በሰበታ ከተማ አስተዳደር በህገ ወጥ መንገድ በቤት ውስጥ የተከማቸ ከ3 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር በላይ እና የውጭ ሀገራት ገንዘብ ተያዘ
‘’የወንድምህ የደሙ ድምፅ ከምድር ወደ እኔ ይጮሀል፤ አሁንም የወንድምህን ደም ከእጅህ ለመቀበል አፍዋን በከፈተች በምድር ላይ አንተ የተረገምህ ነህ’’ (ዘፍጥረት 4፣10-11)
“አዲስ አበባ የክልልነት መብቷ ሊረጋገጥላት ይገባል፡፡|”ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ
በብልጽግና ነውረኞች የተጠለፈው ፍትሕ መጽሔት /ከ እስከ-ማዕዘኑ
ኦሮምያ – በብብቶቿ ፍምና ረመጥ የታቀፈች ምድር –ከበየነ ከበ
ኢትዮጵያ ከኖርዌይ ትበልጥብናለች
የባህር ዳር ከንቲባ የነበሩት መሐሪ ታደሰ (ዶ/ር) ከሥልጣን ርቀው ስለቆዩበት አስገዳጅ ሁኔታ እና የተነሱበትን መንገድ በግልጽ ይፋ አደረጉ ያንብቡት
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ!! የተወደዳችሁ የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች። ከብዙ ወንድምና እህቶቼ ለቀረቡልኝ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት፤ የሚታዩ ብዥታዎችን ለማጥራትና አንዳንድ ከእውነት የራቁ ዘገባዎችን ለማስተካከል የሚከተለውን አቀርባለሁ። ከሁሉ አስቀድሜ በገጠመኝ የቤተሰብ ጉዳይ ከሚገባው በላይ በመዘግየቴ የምወደውን የባሕር ዳር ከተማ ሕዝብ፤ የከተማ አስተዳደሩን ምክር ቤት፤ አብረውኝ የሚሠሩ የከተማ አስተዳደሩን ሠራተኞችና የክልል አመራሮችን ይቅርታ በመጠየቅ እጀምራለሁ። ቤተሰቤ የሚኖረው አዲስ አበባ ነበር። መጋቢት ወር ላይ የልጆቼ ትምህርት ቤት በኮረና ምክንያት በመዘጋቱ ወደ አሜሪካ እንዲሄዱ አድርጌ እኔ ባሕር ዳር ከተምኩ። ነገር ግን ከተለያየን ከሦስት ወር በላይ በመሆኑ ቤተሰቤን ለመጠየቅ ወደ አሜሪካ መሄድ እንዳለብኝ በግንቦት ወር ለክልል አመራሮች አሳወቅሁ። ጉዳዩን በጋራ
The post የባህር ዳር ከንቲባ የነበሩት መሐሪ ታደሰ (ዶ/ር) ከሥልጣን ርቀው ስለቆዩበት አስገዳጅ ሁኔታ እና የተነሱበትን መንገድ በግልጽ ይፋ አደረጉ ያንብቡት appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
የአማራ የምሁራን መማክርት ጉባኤ “የቢጫው ሰራዊት” ፈጠራ ብሎም ሰለባ ሆኗል ብለን ብናስብስ!? (አሰፋ በድሉ)
(ረዘም ያለ ስለሆነ በትዕግስት እንድታነቡት እጋብዛለሁ) ይህን ጉባኤ አንዲሆን የምመኘው ለመሪው ፓርቲ፤ለተቃዋሚ ፓርቲወች፤ለማህበረሰቡ የዕውቀት፤የእውነት፤የጥበብ፤የፖሊሲ ወዘተ…ምንጭ/አመንጭ ማዕከል እንደሂሆን ነው፡፡ለምሁራን ደግሞ እንደ ስሙ የሃሳብ፤የዕውቀት ጉባኤ ወይም መድረክ የሚዘረጋበት ማእከል እንዲሆን ነው፡፡ Think tank body አንደሚባለው፡፡ መተዳደሪያ ደንቡን ስላላየሁ የመምኘውን ነው የገለጽሁት፡፡ ከሰሞኑ በአማራ ክልል፤ የምሁራን መማክርት ጉባኤ፤ ያዘጋጀዉን አዲስ ድረ-ገጽ መልቀቁን እና የአባላት መመዝገቢያ ቅጽ ማዘጋጀቱን አንድ የፌስቡክ ወዳጄ አጋርቶኝ ተመለከትሁት፡፡ (https://amharasc.org/)፡፡የተመለከትሁት አርማ ግን የፈሩት ይደርሳል ነው የሆነብኝ፡፡ የአቅማችንን ለማበርከት የተዘጋጀን ሰወችንም ከበር እንድንቆም አስገድዶናል፡፡ምልክቱ ከዚህ በታች የተመለከተው ነው፡፡ በእነሱ ቤት የከተማ ልጆች እንደሚሉት “አራዳ” መሆናቸው ነው፡፡ ይህ ምልክት ሶስት ነገር ይጠቁመኛል፡፡ አንደኛው ምልክት የክልሉ ብሎም የፌደራል ቋንቋ የሆነውን በአማርኛ ፊደል ምትክ
The post የአማራ የምሁራን መማክርት ጉባኤ “የቢጫው ሰራዊት” ፈጠራ ብሎም ሰለባ ሆኗል ብለን ብናስብስ!? (አሰፋ በድሉ) appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
የብርሃነ መስቀል አበበ ሰኚ አስቂኝ ጭውውት በOMN –አምባቸው ደጀኔ (ከወልዲያ)
ብርሃነ መስቀል አበበ ሰኚ የሚባለው ዐይነ ደረቅ አክራሪ ብሔርተኛ “አማርኛ በኢትዮጵያ 29 በመቶ ብቻ ተናጋሪ ሲኖረው ኦሮምኛ ግን 71 በመቶ ነው፡፡” እያለን ነው፡፡ የት ሄዶና መቼ ይህን ጥናት እንዳደረገ አልገለጸም፡፡ ስድስት ሚሊዮኑን ትግሬ፣ ስድስት ሚሊዮኑን ሶማሌ፣ ስንት ሚሊዮኑን ደቡቤ፣ ስንት ሚሊዮኑን ሽናሻ፣ አገው፣ አኙዋክ፣ በርታ፣ ጉሙዝ ወዘተ. ከአማርኛው ይሁን ከኦሮምኛው የቋንቋ ቅርጫት በየትኛው ውስጥ እንደከተታቸውም አልጠቆመም – ፍጹማዊ የኅሊና መታወር ማለት ይቺ ናት እንግዴክ፡፡ በዚህ ሰውዬ ጥናት መሠረት – ይህንን ከእንስሳም የወረደ ስብዕና ሰው ብሎ መጥራት እንኳን ይቸግረኛል በውነቱ – ከኢትዮጵያ ሕዝብ 71 በመቶው ኦሮሞ ሲሆን 29 በመቶው ደግሞ አማራ ነው፡፡ አዲዮስ ሸዋ! አዲዮስ የለማ አገር ቅምብቢት! አዲዮስ ትላልቅ ከተሞች!
The post የብርሃነ መስቀል አበበ ሰኚ አስቂኝ ጭውውት በOMN – አምባቸው ደጀኔ (ከወልዲያ) appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
እኔንም አማረኝ (ዘ-ጌርሣም)
እኔንም አማረኝ ሩጦ ማሸነፍ ሁሉንም መቅደም ባንዲራ ማውለብለብ በኢትዮጵያ ስም ሕያው ነህ አበበ ሥጋህ ነው የሞተው የተሰናበትከን ማሞን ተክተህ ነው እንኳንስ በጫማ ምቾቱን ጠብቆ የወርቅ ኒሻን ወስዷል በባዶ እግሩ ሩጦ አቻውን በማድከም ልቡን አንቀጥቅጦ የኦሎምፒክ መቅረዝ ከሩቅ ሲንቀለቀል ጋዜጠኛ ሲጮህ ላንቃው እስኪነቀል የኢትዮጵያ ባንዲራ ከፍ ብሎ ሲሰቀል ስሜቱን ገምቱ በህሊናችሁ ውስጥ የልብ ትርታ እንዴት እንደሚረግጥ በደስታ ሰክሮ ስሜት ሲንቀጠቀጥ አሸናፊው ታውቆ በይፋ ሲገለጥ እኔንም አማረኝ ሩጦ ማሸነፍ ሁሉንም መቅደም ባንዲራ ማውለብለብ በኢትዮጵያ ስም ለኢትዮጵያ አትሌቶች ክብር ይሰጣቸው ቅኔና መወድስ ይዘረፍላቸው ከታሪክ ሰዎች ጎን ይመዝገብ ስማቸው ለትውልድ መመኪያ ነውና ሥራቸው ከፍ ብሎ ይሠራ የክብር ሰገነት የኢትዮጵያ አትሌቶች እንዲቀመጡበት የአገር ጀግኖች ተብለው
The post እኔንም አማረኝ (ዘ-ጌርሣም) appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
በባህርዳር ከተማ የተሰራዉ ህገ ወጥ ግንባታ ማፍረስና ህግ የማስከበር ስራ ዉጤታማ እንደነበር ተገልጿል
ይህን አስመልክቶ በባህርዳር ከተማ አስ/ር ም/ከንቲባ አቶ አማረ አለሙን ጨምሮ በሌሎች አመራሮች ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ ስለሆነም ሙሉ ቪዲዮዉን በመከታተል በቂ መረጃ ያግኙ፡፡ Bahirdar city Communication በህገወጥ መከላከል የተሰጠ መግለጫ በባህርዳር ከተማ የተሰራዉ ህገ ወጥ ግንባታ ማፍረስና ህግ የማስከበር ስራ ዉጤታማ እንደነበር ተገልጿል፡፡ይህን አስመልክቶ በባህርዳር ከተማ አስ/ር ም/ከንቲባ አቶ አማረ አለሙን ጨምሮ በሌሎች አመራሮች ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ስለሆነም ሙሉ ቪዲዮዉን በመከታተል በቂ መረጃ ያግኙ፡፡ Posted by Bahirdar city Communication on Monday, September 28, 2020
The post በባህርዳር ከተማ የተሰራዉ ህገ ወጥ ግንባታ ማፍረስና ህግ የማስከበር ስራ ዉጤታማ እንደነበር ተገልጿል appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
ከዘውጌነት ይልቅ ዜግነት ፡ ከአቶ አባተ ካሳ
የዛሬይቱ ኢትዮጵያ በጎሣ/በዘውጌ ፖለቲካና በዜጋ ፖለቲካ ማህል ተከፍላ ትገኛለች። መገንዘብ ያለብን ጎሣ/ዘውግ የሚኖረው ሀገር ሲኖር ስለሆነ ከዘውጌነት ይልቅ የአገር ዜግነት ልዕልና ይኖረዋል። በእኔ እይታ የዜጋ ፖለቲካ አራማጆች የሚታገሉት ኢትዮጵያ እውነተኛ ዲሞክራሲና የሕግ በላይነት የሚከበሩባት አገር እንድትሆን ሲሆን በተጨማሪም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዜግነቱ ሙሉ መብቱ ተከብሮ የሚኖርባት አገር እንድትሆን ነው። [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]
The post ከዘውጌነት ይልቅ ዜግነት ፡ ከአቶ አባተ ካሳ appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
ፖለቲከኞች ነን ባዮች በፖለቲካ ስም የሚሰሩት ታላቅ የታሪክ ወንጀል-ክፍል አራት!! – ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)
ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር) ድንቁርና ከግንዛቤ ድክመት የተነሳ ሊከሰት የሚችል ነው ብሎ መገመት ድንቁርናን ዝቅ አድርጎ መመልከት ነው። ድንቁርና ከዚህ በላይ የሆነ ነው። በጣም ተንቀሳቃሽ፣ ቀናተኛ፣ ስግብግብና ካለአግባብ ለእኔ ይገባኛል በማለት ሀብት የሚያግበሰብስ፣ ዓለምን በጠባብ መነፅር የሚመለከት፣ ካለአግባብ አንድ ድርጊት እንዲፈጸም ትዕዛዝ የሚሰጥ፣ ሌሎችን የሚያገል ነው። በየጊዜው ሃሳቡን የሚለዋውጥ፣ ይሁንና በምንም ዐይነት ተሳሳትኩ ብሎ የማያምን ነው። የወደፊቱን ሁኔታ በሚያሽበርቅ ቀለም የሚስል፤ ቀለሙ ግን ተለዋዋጭ ነው። ድንቁርና የታሪክ አንቀሳቃሽ ኃይል ነው። በዓለም ላይ የተስፋፋ በመሆኑም ማንም ሰው ከዚህ ዐይነቱ በሽታ ሊያመልጥ የሚችል አይደለም። በማንኛውም የቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ከሱ ጋር የማይገናኝ የለም። ስለሆነም ሁሉም በእሱ ፊት እኩል ነው። ከኃያላኖች በላይ ኃያል የሆነ ነው። ዛሬ
The post ፖለቲከኞች ነን ባዮች በፖለቲካ ስም የሚሰሩት ታላቅ የታሪክ ወንጀል-ክፍል አራት!! – ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር) appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
ሕብር ሬዲዮ ከአቶ ተካ ከለለ ጋር በወቅታዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አዲስ ውይይት
ሕብር ሬዲዮ ከአቶ ተካ ከለለ ጋር በወቅታዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አዲስ ውይይት
The post ሕብር ሬዲዮ ከአቶ ተካ ከለለ ጋር በወቅታዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አዲስ ውይይት appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
‹‹ ጦር ይሠበቃል ወይ፣ ጋሻ ለሌለው ሰው!!!›› ‹‹ ወታደር ሀገር እንጂ ብሔር የለውም!!!›› –ፀ/ትፂዮን ዘማርያም
‹‹ወታደር ሀገር እንጂ ብሔር የለውም!!!›› ‹‹የክልል ልዩ ታጣቂ ኃይል ይፍረስ፤ በዘር ተደራጅቶ፣ በዘር የታጠቀ፣ የዘር ፍጅትን ያፋጥናል!›› ያሬድ ሀይለማርያም ኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት የክልል ሥልጣንና ተግባር ‹‹የክልሉን የፖሊስ ኃይል ያደራጃል ፣ይመራል፣የክልሉን ሰላምና ጸጥታ ያስጠብቃል፡›› ይላል አንቀጽ 52፡፡ በህገ-መንግሥቱ መሠረት ክልሎች የፖሊስ ሠራዊት ኃይል ብቻ ይኖራቸዋል ማለት ነው፡፡ የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ( ትህነግ) ህገመንግሥቱ በመጣስ ክልሎች ልዩ ኃይል እና የሚሊሻ አደረጃጀቶች እንዲኖራቸው አደረገ፣ ቀስ በቀስ እየተጠናከሩ በመሄድ በክልሎች መኃል ተጨማሪ ኃይል የማሰባሰብ ክልሎች እርስበእርሳቸው የጎሪጥ እንዲተያዩ አደረጋቸው፡፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን በዘርና በብሔር አደረጃጀት ከፋፈለው፣ ሸነሸነው፡፡ ወያኔ/ኢህአዴግና ኦዴፓ ብልጽግና የሠራዊቱን ሃገራዊ ፍቅሩንና ብሄራዊ ክብሩን በማዋረድ ሠራዊቱን በዘርና ኃይማኖት ፍጅት ውስጥ ተሳታፊ እንዲሆን
The post ‹‹ ጦር ይሠበቃል ወይ፣ ጋሻ ለሌለው ሰው!!!›› ‹‹ ወታደር ሀገር እንጂ ብሔር የለውም!!!›› – ፀ/ትፂዮን ዘማርያም appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
የፌዴራል መንግስቱ ህጋዊነት ከከሰረው ቡድን ቅዥት ሳይሆን ከህገ መንግስቱ እና ከኢትዮጵያ ህዝቦች የመነጨ ነው
በብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሲቪክ ማህበራት ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር አለሙ ስሜ የፌዴራል መንግስቱ ህጋዊነት ከከሰረው ቡድን ቅዥት ሳይሆን ከህገ መንግስቱ እና ከኢትዮጵያ ህዝቦች የመነጨ መሆኑን ገለጹ፡፡ ዶክተር አለሙ ስሜ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ÷ በኢትዮጵያ መስከረም 25ም ሆነ ከዚያ በኋላ ጠንካራ እና ህጋዊ መንግስት አለ ይኖራልም ብለዋል። ዶክተር አለሙ ቀን እየቆጠረ አንዴ ከመስከረም 25 በኋላ ሌላ ጊዜ ከመስከረም 30 በኋላ መንግስት የለም የሚለው ቡድን ህጋዊ ስልጣን የሌለው የቡድን ምኞቱን የሚናገር ስብስብ ነው ብለዋል፡፡ ይህም ሀሳብ ተራ ቅዥት እና ምንም እርባና የሌለው የከሸፋ ሃሳብ ነው ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ተከትሎ የፌዴረሸን ምክር ቤት ህግ መንግስታዊ ትርጉም ሰጥቶበት
The post የፌዴራል መንግስቱ ህጋዊነት ከከሰረው ቡድን ቅዥት ሳይሆን ከህገ መንግስቱ እና ከኢትዮጵያ ህዝቦች የመነጨ ነው appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
በቤንሻንጉል በተፈጸመ ጥቃት ተሳትፎ አላቸው የተባሉ ባለስልጣናት መጥፋታቸው ተሰማ
በመተከል ዞን በተከሰተው የፀጥታ ችግር ውስጥ እጃቸው አለበት የተባሉ እና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባለመወጣት የተጠረጠሩ ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ አመራሮች ላይ ፖለቲካዊ እርምጃ መወሰዱን የክልሉ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይስሃቅ አብዱልቃድር ለቢቢሲ ተናገሩ። የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተከል ዞን የተለያዩ ወረዳዎች አመራር የነበሩ 45 ግለሰቦች ሙሉ በሙሉ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ መደረጉን የተናገሩት ኃላፊው እጃቸው አለበት በሚል ጥቆማ የቀረበባቸው በሕግ እንዲጠየቁ እንደሚደረግ ተናግረዋል። አጠቃላይ በተደረገው በወረዳ አመራር ግምገማ “በተለያየ መንገድ ከፀረሰላም ኃይሎች ጋር እጃቸው አለበት” ተብለው የተጠረጠሩ አመራሮች ላይም እርምጃው መወሰዱን ተናግረዋል። ስራቸውን በአግባቡ አልተወጡም፣ የሕዝብን ደህንነት ማስጠበቅ አልቻሉም፣ መረጃ እያላቸው ቸልተኛ ሆነዋል በሚል ተገምግመው ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ከተደረጉ 45 አመራሮች መካከል በወንጀል ውስጥ በመሳተፍ
The post በቤንሻንጉል በተፈጸመ ጥቃት ተሳትፎ አላቸው የተባሉ ባለስልጣናት መጥፋታቸው ተሰማ appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
የዘር መታወቂያ ካርድ የሚሠጡ የንግድ ፓርቲዎችና የጦር አበጋዞች ሠራዊት ይወገዳሉ!!! –ሚሊዮን ዘአማኑኤል
የደብረፂዮንና የዐብይ ዘረኛ የጦር አበጋዞች መንግሥት አደረጃጀት፣ፍልሚያና ፍፃሜ!!! ዐብይ ሪፓብሊካን ጋርድና መከላከያ ሠራዊት የኦሮሚያ ልዩ የፖሊስ ኃይልና ሚሊሽያ አላቸው !!! ደብረፂዮን አጋዚ ጋርድና አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሽህ ጦር አላቸው!!! አብዲ ኢሌ ሄጎ ጋርድና ልዩ የፖሊስ ኃይልና ሚሊሽያ አርባ ሽህ ጦር ነበራቸው፡፡ አብዲ ኢሌ፣ደብረፂዮንና ዐብይ አንድም ሁለትም ሦስትም ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ዘብ የሚቆምለት ህዝባዊ ፌዴራላዊ ጋርድ፣ ልዩ ኮማንዶ ጠባቂ ጦር አልተገነባለትም ከሱዳን ድንበር አርባ ኪሎሜትር ላይ ሲገኝ የሽምቅ ተዋጊዎች የዘርና የኃይማኖት ፍጅት (ጆኖሳይድ) የሚያደርጉበት አካባቢ መሆኑን ሁሉም ያውቃል፡፡ የዘር መታወቂያ ካርድ የሚሠጡ የንግድ ፓርቲዎችና ሠራዊት ባላቸው አገር የበለጸገ አገር በዓለም ላይ የለም፣ የዘር፣ የብሄርና፣ቀለም ልዩነት፣አስተሳሰብ ኃላቀር ያልሠለጠኑ ሰዎች
The post የዘር መታወቂያ ካርድ የሚሠጡ የንግድ ፓርቲዎችና የጦር አበጋዞች ሠራዊት ይወገዳሉ!!! – ሚሊዮን ዘአማኑኤል appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
እነ እስክንድር ነጋ የዋስትና መብት ተከለከሉ
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ የሕገ መንግሥት እና ጸረ ሽብር ወንጀል ልደታ ምድብ ችሎት አቶ እስክንድር ነጋ እና ሌሎች አራት ተከሳሾችን የዋስትና መብት ውድቅ ሲያደርግ፤ ለአምስተኛ ተከሳሽ ግን የ30 ሺህ ብር ዋስትና ፈቅዷል። የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ የሕገ መንግሥት እና ጸረ ሽብር ወንጀል ልደታ ምድብ ችሎት አቶ እስክንድር ነጋ እና ሌሎች አራት ተከሳሾችን የዋስትና መብት ውድቅ ሲያደርግ፤ ለአምስተኛ ተከሳሽ ግን የ30 ሺህ ብር ዋስትና ፈቅዷል። ችሎቶ የእነ እስክንድር ነጋ ጠበቆችን የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ሕግን ምላሽ አዳምጦ ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 12 ቀን 2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል። ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ማንተጋፍቶትስ ስለሺ ኂሩት መለሰ
The post እነ እስክንድር ነጋ የዋስትና መብት ተከለከሉ appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.
አንጋፋው ፖለቲከኛና የሰብኣዊ መብት ተሟጋች ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም አርፈዋል
አንጋፋው ፖለቲከኛና የሰብኣዊ መብት ተሟጋች ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም አርፈዋል። ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም! ታላቅ ምሁር፣ ሞጋች፣ ደፋር፣ ፈላስፋ፣፣እስከ መጨረሻዋ ሰአት አብዮተኛና የለውጥ ሃዋርያ! ሰውን የማያዳሉ ለእውነት የቆሙ የኢትዮጵያ አድባር ነፍስዎን በአጸደ ገነቱ ለዘላለም ያኑርልን።
The post አንጋፋው ፖለቲከኛና የሰብኣዊ መብት ተሟጋች ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም አርፈዋል appeared first on ዘ-ሐበሻ Latest Ethiopian News and Point of View 24/7.