Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የዞን ዘጠኝና የታሳሪ ጋዜጠኞች ጠበቃ አቶ አምሃ ለቢቢኤን ራድዮ ተናገሩ

$
0
0

“ህገ-መንግስቱ በህግ ጥላ ስር የሚገኙ ታሳሪዎች ከህግ ጠበቃቸው ፡ ከቤተሰቦቻቸው ከቅርብ ወዳጆቻቸው ጋር መገናኘት እንደሚችሉ ቢደነግጉም የማእከላዊ አሳሪዎች ይህን ሊፈቅዱ አልቻሉም፡፡ በእስር ላይ የሚገኙ የዞን ዘጠኝ አባላትና ጋዜጠኞች ጠበቆቻቸውን እንዲያገኙ ፍርድ ቤቱ ትዛዝ ቢያስተላልፍ የማእከላዊ ሃላፊ የሆኑት አቶ ተክላይን ጨምሮ ይህን ለማድረግ ፍቃደኛ አልሆኑም፡፡” የሚሉት ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንን “ይህ ተግባራዊ ካልሆነ ጥብቅና መቆሜን አቆማለሁ ሲሉ” ገለጹ፡፡ የፍትህ ስርአቱም አደጋ ላይ ወድቁዋል ይላሉ ቢቢኤን ሬድዪ ከአቶ አምሃ ጋር ያደረገውን ቆይታ ይከታተሉ::


የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ምርጫ ተጠናቀቀ

$
0
0

debereselam-medhanialem
በርከት ያላችሁ የዘ-ሐበሻ አንባቢያን ዛሬ በጉጉት እየተጠበቀ ያለውን የሚኒሶታውን ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ቀጣይ ሁኔታን የሚወስነውን ምርጫ በተመለከተ ‘ውጤቱ ምን ሆነ?’ ስትሉ በስልክ፣ በኢሜል እና በተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች በጠየቃችሁን መሠረት የቤተክርስቲያኑ አሁን ያለበት ሁኔታን እነሆ።

በፍርድ ቤት በታዘዘው መሠረት ወደ ሃገር ቤቱ ሲኖዶስ እንጠቃለል የሚለውም፤ እንደነበርነው በገለልተኛነት እንቆይ የሚለውም ወገን በድምጽ ብልጫ የቤተክርቲያኑን ሁኔታ ለመወሰን ድምጽ ሲሰጡ ውለዋል። ወደ 5 ፒኤም አካባቢም የድምጽ መስጠቱ ሂደት ተጠናቋል። የፍርድ ቤት ዳኛና ከሁለቱም ወገኖች የተወከሉ ሰዎች ባሉበት የድምጽ ቆጠራው እየተካሄደ ነው።

የድምጽ ቆጠራው ውጤት ዛሬ ማምሻውን ይለቀቅ፤ አይለቀቅ ዘ-ሐበሻ ያወቀችው ነገር ባይኖርም ውጤቱን እንደሰማን ለአንባቢዎቻችን እናቀርባለን።

በምርጫው ውስጥ ከተሳተፉ ወገኖች ለማረጋገጥ እንደቻልነው በሁለቱም ወገኖች የቆሙ ካህናት በየተቃራኒው ወገን ተቃውሞ ሲሰማባቸው ነበር።

ዓባይ እንደዋዛ–“ኢትዮጵያ ሃገሬ ናት፤ ዜግነቴ ኢትዮጵያዊ ነው” ክፍል ሶስት (ከአክሎግ ቢራራ (ዶ/ር)

$
0
0

 

ከአክሎግ ቢራራ (ዶ/ር

ከአክሎግ ቢራራ (ዶ/ር

ክፍል ሁለት ዓባይና ኢትዮጵያ አንድና የተያያዙ መሆናቸውን ያሳያል። አንድና የተያያዙ ናቸው የሚለውን ሃሳብ ከተቀበልን ዓባይ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ እስካገለገለና ኑሮውን እስካሻሻለ ድረስ የኢትዮጵያን ይገባኛልነትና የሚሰሩ መሰረተ ልማቶች መቀበል የኢትዮጵያውያን ግዴታ ነው። ዓባይ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥሪት መሆኑን አምናለሁ። ጎሳዊ ወይንም ክልላዊ ሃብት አይደለም። ስለሆነም፤ ዓባይን የምንታደገው “ኢትዮጵያ ሃገሬ ናት፤ ዜግነቴ ኢትዮጵያዊ ነው”–-[ሙሉውንለማንበብእዚህይጫኑ]—

(ሰበር ዜና) የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ በገለልተኛነቱ እንዲቀጥል የሚፈልገው ወገን አሸነፈ

$
0
0

debereselam Minnesota
አሁን በደረሰን ዜና መሠረት ለረዥም ጊዜ ሲያወዛግብ የቆየው የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ እልባት አግኝቷል። ወደ ሃገር ቤት ሲኖዶስ ይጠቃለል የሚለው ወገን እና በገለልተኛነቱ ይቀጥል የሚለው ወገን ባደረጉት ምርጫ አብዛኛው ሕዝብ በግለልተኛነቱ እንዲቀጥል በመወሰኑ ቤተክርስቲያኑ ባለበት እንደሚቀጥል ታውቋል።

ዝርዝር መረጃውን ይዘን እንመለሳለን።

የሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ የቦርድ አባላት ከስልጣናቸው ወረዱ፤ ቤተክርስቲያኑም በገለልተኛነቱ እንዲቀጥል ተወሰነ

$
0
0

debereselam Minnesota

ይታየው ከሚኒሶታ

ከአንድ ዓመት በላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ ሲያወዛግብ፣ ሲያነጋገር ቆይቷል። “ሃገር ቤት ያለው ሲኖዶስ እና ውጭ ሃገር ያለው ሲኖዶስ እስከሚስማሙ ድረስ ላለፉት 20 ዓመታት በገለልተኛነት እንደቆየነው መቆየት አለብን” በሚለው እና “ወደ ሃገር ቤቱ ሲኖዶስ መቀላቀል ያለብን ጊዜ አሁን ነው” በሚለው ወገን በተነሳው እሰጥ አገባ ሲታመስ የቆየው የሚኒሶታው ደብረ ሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ዛሬ ምላሹን አግኝቷል፤ በድምጽ ብልጫም በገለልተኛነቱ እንዲቀጥል ተወስኗል።

ወደ ሃገር ቤቱ ሲኖዶስ እንዲቀላቀል የሚፈልገው ወገን በአዲስ አበባው ሲኖዶስ ስር ያሉ አባቶችን ጋብዞ የነበረ ሲሆን በተለይ አቡነ ማርቆስ የተባሉ አባት ለ21 ዓመታት የቆየውን ቤተክርስቲያን “ህንጻ’ እያሉ ሲያንቋሽሹ እንዲሁም “መድሃኔዓለም ቤተክርስቲያንን አሳማ ያርቡበት” ሲል አሰድቧል በሚል ከፍተኛ ተቃውሞ ሲደርስበት ነበር። (የቪዲዮ ማስረጃውን ለማየት ይህን ይጫኑ)

ወደ ሃገር ቤቱ ሲኖዶስ እንዲቀላቀል የሚፈልገው ወገን በዚህ ወቅት ከወያኔ ጋር በመቆም አልተሳካም እንጂ በዘ-ሐበሻ ላይም ክስ መስርቶ ነበር። ይኸው ወገን በሌሎች ኢትዮጵያውያን የሚጻፉትን አስተያየቶች እንዲታፈኑ በጠበቃቸው አማካኝነት ደብዳቤ ጽፈው የነበረ ቢሆንም ዘ-ሐበሻ ጆሮ ዳባ ልበስ ብላ ቆይታለች። ጠበቃቸው ለከሰሰችው ክስም ምላሽ አግኝታለች።

በነዚህ ሁኔታዎች የቀጠለው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ዛሬ በሕግ አደባባይ እጣፈንታውን የለየ ሲሆን “እግዚአብሔር አሸንፏል” ሲሉ ምእመናኑ ይገልጻሉ። እንደምእመናኑ ገለጻ “የወያኔ መንግስት ፖለቲካ በማይገባቸው እህትና ወንድሞቻችን ውስጥ በሃይማኖት ተቆርቋነት ስም ገብቶ፤ ካህናቱን በገንዘብ አታሎ ደብረሰላም ውስጥ ያለውን ከ1.7 ሚሊዮን ዶላር እጁ ለማስገባት ያደረገው ጥረት ከሽፏል፤ የወያኔ እቅድ 1.7 ሚሊዮን ዶላሩን በእጅ አዙር ወስዶ ወገንን ለመግደያ ጥይት ማዋል እንደነበር ደርሰንበታል” ብለዋል።

(በማህበራዊ ድረ ገጾች እየተበተኑ ካሉ ፍላየሮች መካከል አንዱ)

(በማህበራዊ ድረ ገጾች እየተበተኑ ካሉ ፍላየሮች መካከል አንዱ)


“እግዚአብሄር ታላቅ ነው” የሚሉት አንድ እናት “ለሰላም እና ለአንድነት ቆመናል። ካህናቱ ሁሉ ከጎናችን እንዲቆሙ ለምነናል፤ በተለይ አባ ሃይለሚካኤል እንደባትነታቸው ብዙ ጠይቀናቸዋል፤ ግን እርሳቸው ‘ቤተክርስቲያኑን ወደ ሃገር ቤቱ ሲኖዶስ መመለስ የቀደመ ህልሜ ነው’ ሲሉ ነግረውናል፤ ያን ግዜ አባ ሃይለሚካኤል ከማን ጋር እንደቆሙ አውቀናል ሲሉ ይናገራሉ።

“በዛሬው ምርጫ በተለይ ላለፉት 20 ዓመታት ታፍራና ተከብራ የኖረችውን ቤተክርስቲያናችንን ከአራቱ የቦርድ አባላት በቀር ሌላው ለሃገር ቤቱ ሲኖዶስ ሊያስረክብ የነበረው ወገን ከስልጣኑ ተጠራርጎ በሕዝብ ድምጽ መባረሩ አስደስቶናል” ያሉን አስተያየት ሰጪዎች የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ወያኔ ያወጣውን ከፍተኛ ገንዘብ በማክሸፍ ለዚህ ድል መብቃቱ አኩርቶናል ብለዋል።

Hiber Radio: አበበ ገላው ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ በጸረ ሕወሃት ትግል ላይ እንዲያተኩሩ ጠየቀ፤ ሌንጮ ባቲ ይናገራሉ

$
0
0
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ህብር ሬዲዮ  ግንቦት 3 ቀን 2006 ፕሮግራም

                እንኳን ለእናቶች ቀን አደረሳችሁ !

<<…ተከፋፍሎ ለውጥ ያመጣ የለም ።ሰሚም የለም ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ስር ነቀል ለውጥ ነው የሚጠብቀው ። ይህን ለውጥ ለማምጣት በአንድ ላይ መቆም ያስፈልጋል  …>> - ጋዜጠኛና አክቲቪስት አበበ ገላው (ሙሉውን ያዳምጡት )

<<…ሊያሳስበን የሚገባው መንግስት መተካት ብቻ አይደለም። …ኢትዮጵያ የተጠመደ ፈንጂ ላይ ያለች አገር ነች…>> - አቶ ሌንጮ ባቲ የኦሮሞ ዲሞክራሲአዊ ግንባር ቃል አቀባይ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለሕብር ከሰጡት ቃለ ምልልስ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት

<<…ስደትና እናትነት ከባድ ነው። …የ ናቶች ቀንን ለማክበር የመጀመሪያዬ ነው…>> - ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል የዕናቶች ቀንን ምክንያት ካደረግነው ቆይታ የተወሰደ

ድምጻዊ ይሁኔ በላይ በቬጋስ ሕይወት ለማዳን በተደረገ የሙዚቃ ዝግት ላይ ተገኝቶ በነጻ ዘፈነ

አዲስ አልበም  እየሰራ ነው  (ከይሁኔ ጋር አጭር ቆይታ አድርገናል)

 

 ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

ረዳት አብራሪ ሀይለመድህን አበራ በስልጣን ላይ ላለው  አገዛዝ ተላልፎ አይሰጥም ተባለ

በኦሮሚያ ክልል የተፈጸመውን ግድያ የሚቃወም የተቃውሞ ሰልፍ በመላው ዓለም ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጋዜጠኛ አበበ ገላው ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ በጸረ ሕወሃት ትግል ላይ እንዲያተኩሩ ጠየቀ

የሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ የኮሚቴ አባላት መከላከያ ምስክሮች መሰማት ሊጀምሩ ነው

ሶስት የግብጽ ዜጎች በስለላ ተጠርጥረው ታሰሩ

አዲስ አበባ ላይ የተፈራረሙት የደበብ ሱዳን መሪዎች ተዳግም ወደ ተኩስ ገብተዋል

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

ጥሩ የመንፈስ ፍላጎትን አድምጭነት –ልዩ መክሊት ነው –ለእኔ። (ሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 12.04.05 (ሲዊዘርላንድ ዙሪክ)

ዛሬ እንዲህ ወደ ሀገረ አሜሪካ ጉዞ አማረኝ። ስለምን? የንግግር ሥነ – ጥበብ ህግጋት መከበሩ መንፈሴን ስለገዛው።

Commentሥነ – ንግግር ጸጋ ነው። ሥነ – ንግግር ሙያም ነው፤ ሥነ – ንግግር ሁለት መንትያ ልጆች አሉት። እንደ ቤተሰብ የሚያቸውም የቅር ሥጋዎቹ አሉት። ሥጋዎቹን በቀጠሮ ልተውና የሥነ – ንግግር ባላና ወጋግራ የሆነው ጉልቻው ያፈራቸውን ልጆች እስኪ በጥቂቱ እንይ። የመጀመሪያ ልጁ „ተናጋሪ“ ይባላል። ሁለተኛ ልጁ ደግሞ „አድማጭ“ ይባላል። ሁለቱም እንደ ጸጋነታቸው በክህሎት ሊዳብሩ፤ በሥልጠና ክህሎታቸው ጥንግ ድርብ የሆነ ብቃትን ሊጎናጸፉ ይችላሉ። ሁለቱንም የተሰጣቸው ፍጡራን የታደሉ ናቸው። ወይንም አንዱን ብቻም የተሰጣቸው ግማሽ እድለኞችም ሊኖሩ ይችላሉ። በሌላ በኩል አንዱ ደመቅ ብሎ ዘለግ ሌላው ደግሞ ዝቅ ያለ ሁነትም ይገጥማል። ይህ በሂሳብ ስሌት ሩቦ የጎደለው ወይንም ሦስት አራተኛው የተሟላ እንደ ማለት፤ ወይንም ሶስቱ እጅ እንደማለት …..

 

የሥነ ንግግር ጥበብና ዕድገት ዝርዝር ሁነቶች፣ የአንድን ጥሩ ተናጋሪ መስፈርቶችን በሚመለከት 8ኛ መጸሐፌ ላይ ከተገናኘን መጠንኛ ግንዝቤ ለማስገንዘብ ትንሽ ነገር ብያለሁ። ስለዚህ ዘርዝር ያሉትን ነገሮች ገታ አድርጌ አሁን ወደ ተነሳሁበት መሰረተ ሃሳብ ስንሄድ፤ እንደ ህዝብ የኢትዮጵያ ህዝብ ጥሩ ተናጋሪም፤ ጥሩ አድማጭም መሆኑን  አሁን ለተነሳሁበት መሰረታዊ ጭብጥ ይመቸዋል። በነፍስ ወከፍ ስመጣ በሥነ ንግግር ህግጋት መስፈርቱን ያማሉ አብሶ አድማጭነት ቁሞ በእግሩ ሲሄድ ያዬሁት በጓድ ገ/መድህን በርጋ ነበር። ጓድ ገ/መድህን በርጋ የሀገር ውስጥ ንግድ ሚ/ር ቋሚ ተጠሪ፤ የጎንደር ክ/ሀገር ኢሠፓ ኮሜቴ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ፤ በኋላም የሚዛን ተፈሪ ክ/ ሀገር የኢሠፓ ኮሜቴ ተጠሪ የነበሩ ናቸው። የጓድ ገ/መድህን ጥሩ ተናጋሪነታቸው ንጥርነት የመነጨውም ቃላቶች ቢደረደሩ ሊገለጸው ከማይቸለው የምድመጥ ወደር የለሽ መክሊታቸው ነበር። የጓድ ገ/መድህንን የማድመጥ ሥነ ውበትን ለመተንተን ብዕሬ አቅም ፈጽሞ የላትም። የሥነ ንግግር ሙሉዑነት ብቃታቸው ፏፋቴ  ፍጽምና የተላበሰው ከማድመጥ መክሊታቸው ይቀዳ ነበር። አባይን ከምንጩ ከአናቱና ከሞገዳማ ፏፏቴው ጋር እሰቡት – እንደዛ ነው።

 

የጋዜጠኛ አበበ ገላው ፍላጎቱን የመደምጥ ብቃቱ የማዬው እኔ ከዚህ አንጻር ነው። በአፍሪካ ቆይታው የገጠመውን ዕድል ሳያሳልፍ ውስጡን በጥቂቱ ከፈት አድርጎ በጥንቃቄ ለሄሮድስ መለስ ዜናዊ የመጀመሪያ ቴስት የሰጠበት ነበር፤ በኋላም ሁኔታውና አጋጣሚሚውን ሳያሾልክ ወይንም ሳይዘል የመንፈሱን ፍላጎት ድምጸት አደባባይ አውሎ በድምጹ ብቻ ፈቃደ እግዚአብሄር የሰጠውን ታላቅ ኃላፊነት ታምርም ተወጣ። ያ የሬገን ህንፃ ሞገዳማ ድምጽ በጣም ብዙ ትርፍ አስገኝቷል። እርግጥ ውጤቱ የመንፈስ ስለሆነ በኪሎ ወይንም በጆንያ ወይንም በወራንታ መለካት አይቻልም።

 

እኔ እንዲህ እላላሁ፤ የሰው ልጅ መጀመሪያ የተሰጠውን ጸጋ ማወቅ አለበት። ሁለተኛው ደግሞ የተሰጠውን ጸጋ ለመፈጸም መፍቀድ አለበት። ሶስተኛው የተሰጠውን ጸጋ ለማድመጥ የተመቼ መሆን አለበት። አራተኛው የተሰጠውን ጸጋ ለመፈጸም የሚያስችሉ ሁኔታዎችን፣ ወቅቶችንና፣ አካባቢዊ አምክንዮችን ገምቶ መወሰን – መቆረጥና ከትክለኛው የፍላጎቱ ድምጽ ጋር መገናኘት ያስፈልገዋል። ሦስቱንም ጊዜም ጋዜጠኛ አበበ ገላው በተግባር አንቆጥቁጦታል። ጸጋው ይህ ነው፤ መክሊቱ ይህ ነው። ከሰማዬ ሰማዬት የተሸለመው የቤት ሥራውም ይህው ነው።

አቤዋ በእጁ በገባ ማናቸውም አጋጣሚ ሁሉ የፍላጎቱን እንብርት ለማሟላት አብዝቶ የሚባትል፤ ለትውልዱ የረቀቀ ሥጦታ ነው። አብሶ ወጣቶች አብነትነቱን ተከትለው መሰሉን ተግባር ለመከወን ከተጉ፤ ኢትዮጵያ ሀገራችን ፈተናዋም ሆነ የመፍትሄ መንገዶቿ ቀና ይሆናሉ። ለዚህም ነው በ2013 ዘሀበሻ አዘጋጅቶት በነበረው „አመታዊ የምርጥ ሰው“ የድምጽ አሰጣጥ ሥርዓት ላይ እኔ አንደኛ ጋዜጠኛ አበበ ገላውን፤ ሁለተኛ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን፤ ሥስተኛ አቶ ገ/መድህን አርያን አቅርቤ የነበረው። መጨረሻ ላይ „ማገዶው አቶ አንዶአለም አራጌ“ ማሸነፉም አስደስቶኛል።

 

አሁን ወደ ቀደመው። ቀደም ብዬ ያነሳሁትን ነጥብ መንገድ የተከተለው ጋዜጠኛና ገጣሚ ሳዲቅም በሀገረ አሜሪካ አቮይን ቀልባቸውን ገፎ ቁፍ ያላች ዶሮ አድርጓቸዋል። እነዚህ ወጣቶች ለእኛ ልዩ ምልክቶቻችን፤ የተግባር አርማዎቻችን፤ የድርጊት አዛውንቶቻች፤ የሥራም ልዩ እርስቶቻችን ናቸውና ከልብ ልናከብራቸው፤ ልናደንቃቸው ይገባል። የእውነት አሳራቶቻችንም ናቸው።

 

የማከብራችሁ ወገኖቼ የሰው ልጅ ለራሱ መኖር ከፈለገ ሁሉም ይሆናል። መንገዱም እጅግ ሰፊና በድሎት የሰገረ ነው። ይህን አሻም ላላ፤ የህዝብ ዕንባ ለሚጎረብጠው፤ እራሱን ፈቅዶ በመስጠት ኑሮውን የኮረኮንች – የዳገት – የፈተና ለማደረግ ፈቅዶ፤  ለምልዕትና ለሀገረ ኢትዮጵያ  ዕንባ ቅርብነቱን በድርጊት ለሚያቀልም ጀግና ውሎው አዳሩ በፈቀደው የዕንባ ዙሪያ ይሆናል። ይህ ደግሞ መታደል ነው። እኔ እንደማስበውም ምድራዊም ብቻ አይደለም። መዳህኒታዓለም አባታችን ፍቅሩን የገለጸበትን ሚስጥር በአምሳሉ በፈጠራቸው ፍጡራን ሲይ፤ እንዲህ መስዋዕትነቱ መክኖ አለመቅረቱን ሲመለከት በሰማይ ሳይቀር ታላቅ ደስታ ይሆናል። ሁልጊዜም ለተገፋ፤ ለተጨቆነ፤ ባሩድ በዬዕለቱ ለሚቀቅለው ወገን መጮኽ — መጮኽ  —- መጮህ —- መጮኽ ——- መጮኽ ———- ከዶሮ ጩኽት – እስከ ዶሮ ጩኽት ———ጩኽቱ እስኪሳማ ድረስ መጮኽ —- አሁንም መጮኽ —— ነገም መጮኽ —— ከነገ ወዲያም መጮኽ — የቅኑ አቤዋ መንገዱ ይህ ነው። የተፈቀደለትም ይኽው ነው። ወደ ፋመው ፈተና ፈጥኖ መገስገስ …. ስለሆነም ስለ ህዝብ ፍቅር አቤዋ መጻፍም መናገርም ይችላል። ሙሉዑ መብት አለውና! ሆኖታል – ተገኝቶበታል፤ ተስጥቶታልም።

 

አቤዋ አብዝቶ ቅን ነው። ሰውን በጣም ያምናል። ማንንም – በምንም ሁኔታ ይመጣል ብሎ አይጠረጥርም። ንጹህ ፍንትው ያለ ልብ አለው – ወገኖቹን በፍቅር የሚያቀርብበት፣ ፕሮቶኮል ሆነ ሲናርዮ ግጥሙ አይደለም። የወገኖቹ ጉዳይም ባለቤትነት አብዝቶ ይሰማዋል። የፈለገ ከመጠን ያለፈ ቢሆን ድካም ዝር አይልበትም – በተለይ ለችግር ቅርብ ነው። ክብርና ኩራትም አይሻም። ጥሩ አድማጭ ነው። ከግለሰብ ጀምሮ የአካሉን ችግርን ለመጋራት የወደደ ነው። ወገኖቹ ስለሚያደርጉት መልካም ነገር አንደበቱን ከፍቶ ያደንቃል – ያበረታታል – ተስፋ ይሆናል – ስለነገ ብሩህ ቀን ዘለግ አድርጎ በጎ ያስባል – አውንታዊ ነው። እንደ ታናሽነቱም ቀልጣፋ ታዛዥም ነው። ድፍረቱ ያጠግባል፤  የማይመቸውን ነገር ፊት ለፊት ወጥቶ ይናገራል – ስለሆነም የግንባር ሥጋ ነው። በጋዜጠኝነት ሙያ ላይ ለተሰማሩት ወገኖቹ ለሚታሰሩት –  ለሚሰደዱት – ለሚገፉት – ለሚገለሉት ደግሞ ማገራቸውና ልዩ ድምጻቸው ነው። የሙያ ቤተሰቦቹን እንደ እራሱ የአብራክ ልጆቹ ነው የሚያያቸው የትም ይኑሩ የትም። ጠበቃቸው – ዋቤያቸውም ነው። እውነትን አቤ ይወዳል። አቤ የኢጎ በሸተኛ አይደለም። ያልተገባ ክብር ፈጽሞ አይሻም – አይቀበልምም። አሁን እኔ „ጋዜጠኛ“ ከሚለው ቃል በተጨማሪ አንዲት ቃል ባክል አይፈልግም – አይወደውም።

 

እጅግ የማከብራችሁ የሀገሬ ልጆች  እግዚአብሄር አምላክ የሰውን ልጅ ሲፈጥር እንድናመሰግነው ብቻ እንጂ እሱ ምን ጎድሎበት? ከእኛስ ምን የሚፈልገው ነገር ኖሮ? ጋዜጠኛ አበበ ገላው  እንደ አናንያ፣ እንደ አዛርያ፣ እንደ ሚሳኤል ገብቶ ከጋመው እሳት የተማገደው፤ ኑሮው የተበተነው፤ ከቦታ ቦታ የተንካራተተው እለበቃ ብሎ እንሆ ዛሬም የአለሙን መሪ ፕ/ ባራክ ኦባንም መድረክ ላይ መጎተ። ህሊናቸውን ፈተነ። መንፈሳቸው ላይ በትልቁ ጥያቄ ምልክት በቃለ አጋኖ አስቀመጠ። ተባረክልኝ ወንድምአለም – የእኔ ብርቅ ታንሽዬ።

 

የእኔ ክብረቶች ወገኖቼ —  ዕንባ እንዲህ – ይደመጣል። ዕንባ እንዲህ  ይተረጎማል – በትውልዱ። የዛሬ ጹሑፌ መሰረታዊ አላማ አቤዋን እግዚአብሄር ይስጥልን እናትዬ፤ ኑርልን የኔ አባት፤ ድንግልዬ ጥላ ከለላ ትሁንልህ፤ አንተ ኩራት ነህ ለማለት ነው። አቤዋ „ጠንቃቃነት ያተርፋል እንጂ አያከስርምና፤ ከሰማይ በታች ባለ ነገር ሁሉ አደራ ጠንቃቃ ሁን!“ ጦርነቱ የእርስ በእርስ ነው። በዚህ ውስጥ የማይታዩ ዲቃላ ፍላጎቶች፤ የከሱ የሚመስሉ አንገታቸውን ደፍተው የታቆሩ ጥቁር ስሜቶች፤ ኮሳሳ መስለው ቀን የሚጠብቁ ሴራዎችም ሊኖሩ እንደሚችሉ ምንጊዜም ማሰብና ስንዱ መሆን ይሻል። ቅንነትን ማስንበት የሚችለው መኖር ሲቻል ብቻ ነው። ለመኖር ደግሞ በተጓዳኝ ያሉ ነገሮችን ሁሉ በማስተዋል ጥንቃቄን ገበራቸው ማድረግ መሰረታዊ ነው። ከዚህ የበለጡ ህዝበ ጠቀም ተግባራትን ሆነ ገድላትን መፈጸም የሚቻለው በህይወት መኖር ሲቻል ብቻ ነው። እርግጥ አንድዬ አለ። ፈጣሪ አምላክ የሰጠውን ለማቆዬት ጥበቃው ይኖራል። ነገር ግን ሰውም የተገባውን ያህል ለራሱ ጥንቃቄ ማደረግ አለበት። ጥንቃቄ በራሱ ነገን ይወልዳልና።

መከወኛ። አቤዋ! ሁልጊዜም አንተ እሳት ውስጥ ገብተህ መርመጥምጥ የተፈጠርክበት፤ እግዚአብሄር አምላክ መርቆና ቀብቶ የሰጠህ ብቸኛው መንገድህ፤ ቀበቶህም ነውና መልካምና ቀጣይ የመስዋዕትነት ጊዜ – ከድል ጋር እህትህ -አድናቂህና አክባሪህ ተመኘሁልህ። ቤተሰብህን እግዚአብሄር አምላክ ጥበቃ ያድርግ። አሜን።

 

የኔዎቹ በ8.04.2014 በነበረኝ የራዲዮ ፕሮግራምም ስለ አቤዋ በተደጋጋሚ ያልኩት ነገር ነበረኝ። ወፊቱ ሹክ ብላኝ ይሆን? አላውቅም። ብቻ ግን ማድመጥ ትፈልጋላችሁ? መልሱ „ተገኝቶ ነው“ አላችሁ አይደል። የቀረ የለም ዝልዝሉ ጥበሱ ድውለቱ ሽሮም ጨጨብሳውም ያቺ ልስልስ እጅ ቁርጥም የምታደርገው ቡላዬም አለች  www.tsegaye.ethio.info Aktuell Radio Lora www.lora.ch.tsegaye ጎራ በሉና ዘንጣፌ ጤፍ እንጀራ ጋር ታደሙ። ግን ትእዛዝ አይደለም ማስታወስ …. መንፈስን በስንቅ ለሚያኖሩት የመስዋዕትንት ውዶቻችን እንዲሁም እናንተስ ልምን ይቅርባችሁ፤ ናፍቆት የሆናችሁትን አድማጮቼን ጨምሮ አባታችን ይጠብቅልኝ። አሜን! ጨረስኩ – ለዛሬ።

 

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር!

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

 

“መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ”መጽሐፍ ላይ የተደረገው ውይይት


የመደብ ወይስ የብሄር ጭቆና?! (ከአብርሃ ደስታ)

$
0
0

እንዲህ ተጠይቋል
“ባለፉ ስርዓታት የነበረ የማሕበረ ፖለቲካ መዋቅር የመደብ የትግል (ጭቆና) መሰረት ያደረገ ነበር ወይስ ብሄር?”
ባለፉ ስርዓታት ጭቆና ነበረ (አሁንም አለ)። በኢትዮጵያ ታሪክ በህዝብ የተመረጠ ህዝብን ለማገለግል የተነሳ መንግስት አልነበረም (የለም)። ስለዚህ ጭቆና አለ። ጭቆናው ምን መሰረት ያደረገ ነው? ብሄር ወይስ መደብ? በኔ እምነት ጭቆናው ከሁለቱም ዉጭ ነው። በኢትዮጵያ የመደብ ጭቆና አልነበረም (የለም)፤ የብሄር ጭቆናም አልነበረም (የለም)። የነበረው (አሁንም ያለው) ጭቆና የኤሊት (Elite) ጭቆና ነው።
እስካሁን ድረስ የመደብ ፖለቲካ የለንም። የመደብ ፖለቲካ ከሌለ የመደብ ጭቆናም የለም። የብሄር ጭቆናም አልነበረም፣ የለም፣ ሊኖርም አይችልም። የመደብ ጭቆና ግን ለወደፊቱ ሊኖር ይችላል።
ያለፉ የኢትዮጵያ ገዥዎች ስልጣን ለመያዝ እንዲሁም በስልጣን ለመቆየት ሲሉ በህዝቦች ላይ በደል አድርሰዋል። በደል ሲያደርሱ ብሄር ወይ መደብ መሰረት አድርገው አይደለም። መደብ ጭራሽኑም አልነበረም፣ የለም። ብሄር ነበር፤ ግን ጭቆናው ብሄር መሰረት ያደረገ ሳይሆን ስልጣን መሰረት ያደረገ ነበር፣ ነው። የኢትዮጵያ ፖለቲካ Class Based Or Nation Based Struggle ሳይሆን Elite vs People Based Power Struggle ነው።
ገዥዎች ስልጣን መያዝና እስከ ህልፈታቸው በስልጣን መቆየት ይፈልጋሉ። ለስልጣናቸው ሲሉ ታድያ ይደግፈናል የሚሉትን የሕብረተሰብ ክፍል ይጠቅማሉ፤ ለስልጣን አደጋ ነው በሚሉት ህዝብ ወይ ግለሰብ ደግሞ ጉዳት ያደርሳሉ፤ ስልጣናቸውን ለማጠናከር። ግን በፖለቲካ አንድን የሕብረተሰብ ክፍል መጥቀም አይቻልም፣ ይከብዳልና። ስለዚህ በሕብረተሰቡ ስም የተወሰኑ ግለሰቦች እንዲጠቀሙ ይደረጋል። ግለሰቦቹ ሲጠቀሙ የመጡበትን ሕብረተሰብ እንደተጠቀመ ተድርጎ ይታሰባል: ለፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ሲባል። ህብረተሰቡ በስልጣን ላይ ያለ ስርዓት “የኛነት” ስሜት ያሳድራል። ለዚህም ፕሮፓጋንዳ ይሰራል። ምክንያቱም የተወሰኑ ግለሰቦች ብቻ ነው መጥቀም የሚቻለው። ለስልጣን የሚረዳው ግን አብዛኝው ህዝብ ነው። ተጠቃሚ ግለሰቦች ታማኝ የስርዓቱ አገልጋዮች ይሆናሉ። በነሱ ታማኝነት ስርዓቱ ዕድሜው ያራዝማል።
ለስልጣን አደጋ የሚሆን ግለሰብ ወይ ማሕበረሰብ ደግሞ የጥቃት ዒላማ ይሆናል። የስልጣን ዒላማ የሚሆነው በመደቡ አልነበረም (በመደቡ ዒላማ ሊደረግ ይችላል ግን መደብ አልነበረም)። በብሄሩም አልነበረም። በግዜው ካልተመቱ የስልጣን ስጋት ይሆናሉ የተባሉትን ግለሰቦች ወይ የሕብረተሰብ ክፍሎች ይጠቃሉ፤ ብሄራቸው ምን ይሁን ምን። ግን በኢትዮጵያ ታሪክ አንዳንድ ብሄሮች የከፋ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ለምን? በብሄራቸው ምክንያት? አይደለም። ለስርዓቱ ታማኝ አይደሉም፤ ስጋት ይሆናሉ ስለተባሉ ብቻ ነው።
በኢትዮጵያ ታሪክ የመጎዳትም የመጠቀምም መስፈርት ብሄር ወይ መደብ አይደለም፤ የፖለቲካ ታማኝነት (Political Patrimonial-ism) ነው። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ልምድ መሰረት የፖለቲካ ታማኝነት የሚገናኘው ከብሄር ጋር ነው። ሙሉ በሙሉ ባይባልም አንድ ዓይነት ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች የበለጠ ይተማመናሉ (ምክንያቱም ፖለቲካችን መርህ መሰረት ያደረገ ሳይሆን ስሜት መሰረት ያደረገ ነው። በስሜት መነዳት ደግሞ አለመሰልጠን ነው)። አማርኛ ተናጋሪ ስልጣን ከያዘ አማርኛ የሚናገረውን (ሌላ ቋንቋ ከሚናገር) የበለጠ ያምናል። ኦሮምኛ ተናጋሪ ኦሮሞን የበለጠ ያምናል። ትግርኛ ተናጋሪ ትግራዋይን የበለጠ ያምናል። በዚህ መሰረት አማራኛ ተናጋሪ ስልጣን ሲይዝ አማራዎችን ያስቀድማል (ለስልጣኑ ሲል)። ሌሎች ደግሞ ቅሬታ ያድርባቸዋል። ከዛ ለስርዓቱ ታማኝ አይሆኑም። ታማኝ ካልሆኑ በጠላትነት ይፈረጃሉ። በጠላትነት ሲፈረጁ ተጎጂ ይሆናሉ። እነዚህ የስርዓቱ ተጠቃሚ የሚደረጉ ታማኞች ግለሰቦች ናቸው። ብሄር ሙሉ ተጠቃሚ ማድረግ አይቻልምና። ተጎጂዎች ግን ብሄር ሙሉ ወይ የሀገር ህዝብ በሙሉ ሊሆኑ ይችላሉ። ስለዚህ ተጠቃሚዎች ታማኝ ግለሰቦች ናቸው። ተጎጂዎች ግን ብሄር ሊሆኑ ይችላሉ። አንድን ብሄር ሌላኛው ብሄር እየበደለ ነው ይባላል። በዳዮቹ ግን ኤሊቶች (elites) ናቸው። ይህን ነገር ጉዳዩ የብሄር ጭቆና ያስመስለዋል። የብሄር ጭቆና ሊኖር ግን አይችልም።
ስለዚህ ባለፉ ስርዓታት (አሁንም ጭምር) በህዝቦች የሚደርስ በደል አለ። ይህንን በደል ብሄሮች የሚፈጥሩት አይደለም። ያለው በደል በብሄሮች ላይ የተፈፀመ የelites በደል ነው። ኦሮሞዎች የተበደሉ ኦሮሞ ስለሆኑ አልነበረም። ለተመሰረተው ስርዓት ተቀብለው አሜን ብለን እንዲገዙ ለማድረግ የተቃጣ ጥቃት ነው የተፈፀመባቸው። ስለዚህ ጥቃቱ ስልጣን መሰረት ያደረገ ነው። ዒላማው የፖለቲካ ታማኝነትን መሰረት ያደረገ ነው።
አማርኛ ተናጋሪ ንጉሶች ታማኝ ባልሆነ ማንም ሰው እርምጃ ይወስዳሉ። ለዚህም ነው በሁሉም ህዝቦች (አማራን ጨምሮ) በደል የደረሰው። ትግርኛ ተናጋሪ ገዥዎች ታማኝ ባልሆነ ማንኛውም ሰው እርምጃ ይወስዳሉ፤ ለስልጣን ሲሉ። ምሳሌ ህወሓት የትግራይ ልጆች በሆኑ እነ ስየ አብርሃ፣ አውዓሎም ወልዱ፣ አስገደ ገብረስላሴና ሌሎች ታጋዮች ላይ መጥፎ እርምጃ የወሰደው እነኚህ ሰዎች ትግርኛ ተናጋሪ ስላልነበሩ አይደለም። ለስርዓቱ ታማኝ ስላልሆኑ እንጂ።
ስለዚህ በኢትዮጵያ ምድር የደረሰውን እንዲሁም እየደረሰ ያለው ጭቆና ብሄር ወይ መደብ መሰረት ያደረገ ሳይሆን የፖለቲካ ታማኝነት መሰረት ያደረገ ነው። ስለዚህ የኢትዮጵያውያን ጭቆና የብሄር ወይ የመደብ ሳይሆን የፖለቲካ ነው።
It is so!!!

በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች እሥራቶች መካሄዳቸውን የኦፌኮ መሪ ገለፁ

$
0
0

ሰሎሞን አባተ

74ነቀምቴና ሃረማያን ጨምሮ በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የፀጥታ ኃይሎች ትናንትና ዛሬ በሰዉ ላይ ድብደባና እሥራት እየፈፀሙ ነው ሲሉ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ፀሐፊ አቶ በቀለ ነጋ ተናግረዋል፡፡

አቶ በቀለ ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ በምዕራብ ሸዋ በግንደበረትና ጀልዱ፤ እንዲሁም ምሥራቅ ሸዋ አርሲ ነገሌ ተማሪዎች እየተያዙ መታሠራቸውን በወለጋ፤ ነቀምቴም ብዙ ሰው እየተያዘ መታሠሩን ገልፀዋል፡፡

ትናንት ደግሞ ከሃረማያ ዩኒቨርሲቲ አሥር ተማሪዎች ከየማደሪያቸው በፖሊሶች መወሰዳቸውን አቶ በቀለ አክለው ገልፀዋል፡፡

ፓርቲያቸው ሁኔታውን ለመንግሥት ለማቅረብ እየተዘጋጀ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

ከመንግሥት አካላት ስለጉዳዩ ማብራሪያ ለመጠየቅ ተደጋጋሚ ሙከራዎች ቢደረጉም ለጊዜው አልተሣካም፤ ምላሽ በተገኘ ጊዜ እናወጣለን፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Source: voanews

በሊቢያ በርካታ አስከሬኖች ተገኙ

$
0
0

ኢሳት ዜና :-ከሳምንታት በፊት በርካታ ስደተኞችን ጭና ከሊቢያ ወደ ጣሊያን ስታምራ በሰጠመችው ጀልባ ተሳፍረው የነበሩ ሰዎች ሳይሆን እንዳልቀረ የተገመተ አስከሬን መገኘቱን የሊቢያ የአደጋ መከላከ ሰራተኞችን በመጥቀስ ዓለማቀፍ ሚዲያዎች እየዘገቡ ነው።

የሊቢያ አደጋ መከላከል ሰራተኞች በጀልባዋ ከ150 በላይ ስደተኞች ተሳፍረው እንደነበር ለ አል ጀዚራ የገለጹ ሲሆን፤ እስካሁን የተገኘው ግን የ 20 ዎቹ አስከሬን

አበዛኞቹ ተሳፋሪዎች ከአፍሪካ የመጡ እና በሊቢያ በኩል ወደ ጣሊያን ለመሻገር የሞከሩ ስደተኞች እንደሆኑ ተመልክቷል።

እስካሁን 20 አሰከሬኖችን ከባህር ውሰጥ ያወጡት የሊቢያ አሰከሬን ፈላጊዎች፤ ቀሪዎቹን ወደ 130 የሚገመቱ ተሳፋሪዎች አስከሬን ለማውጣት እርዳታ ይደረግላቸው ዘንድ ጠይቀዋል።

ቢቢሲ ከዚሁ ጋር ተያይዞ እንደዘገበው በዚህ ዓመት ከመላው ዓለም ወደ አውሮፓ የሚሻገሩ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ እና በአስደንጋጭ ደረጃ ጨምሩዋል።

ካላፈው የፈረንጆች ዓመት መግቢያ እስከ አፐሪል ድረስ ባሉት አራት ወራት ብቻ 42 ሺህ ስደተኞች በህገ ወጥ መንገድ ወደ አውሮፓ መሻገራቸውን ያመለከተው ቢቢሲ፣ከነኚህ መካከል 25 ሺ 650 የሚሆኑት በሊቢያ ድንበር አድርገው ወደ ጣሊያን የገቡ መሆናቸውን ጠቀሱዋል።

በተለይ በሰሜን አፍሪካና በአረቡ ዓለም የተቀጣጠሉት አብዮቶች ለስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መጨመር ዋነኞቹ ምክንያቶች እንደሆኑ ተጠቅሱዋል።

 

ethsat radio

Health: HPV ክትባት አብዛኛውን የአባለዘር እከክ (Genital Warts) እና አብዛኛውን የማኅጸን ነቀርሳ (Cervical Cancer) ለመከላከል ያስችላል

$
0
0

ስለ HUMAN PAPILLOMAVIRUS መረጃ

የአባለዘር (Genital) human papillomavirus (HPV) በአሜሪካ በጣም የተለመደ፣ በአባለ ዘር ንክኪነት ምክንያት የሚተላለፍ በሽታ ነው። ወደ 100 ዐይነት የሆኑ HPV አሉ። አብዛኛዎቹ ተላላፊ በሽታዎች አንዳችም ዐይነት ምልክት የማያሳዩ እና በራሳቸው የሚጠፉ ናቸው። HPV በሴቶች፣ የማኅጸን ነቀርሳ (cervical cancer) የሚያስከ ትልና በጣም ዝቅተኛ በሆነ ሁኔታ በወንዶችና በሴቶች ጭምር በጣም ያልተለመደ ዐይነት ነቀርሳ ያስከትላል። በተጨማሪም በአባላ ዘር ላይ ኪንታሮት፣ እንዲሁም በላይኛው የእስትንፋስ ማስተላለፊያ ቧንቧችን (upper respiratory tract) እከክ መሰል ኪንታሮቶችን (warts) ያስከትላል። የ HPV በሽታ ምንም ዐይነት መድ ኃኒት የሌለው ሲሆን፣ የሚያስከትለው ችግር ግን በሕክምና ሊድን የሚችል ነው።

hpv virus
በዩኤስ በየዓመቱ ወደ 20 ሚሊዮን የሚጠጉ ስዎች እና ወደ 6 ሚሊዮን የሚሆኑ ተጨማሪ ሰዎች በበሽታው ይጠቃሉ። የ HPV በሽታ በግብረ ሥጋ ንክክ አማካይነት ይተላለፋል። ከ 50% ወይም እጅ በላይ የግብረ ሥጋ ተግባር ማካሄድ የሚያካሂዱ ወንዶችና ሴቶች በሕይወታቸው አንዴ በ HPV ጠንቅ ይለከፋሉ። በዩኤስ በየዓመቱ 12,000 ሴቶች የማኅጸን ነቀርሳ የሚይዛቸው ሲሆን ከዚህ ውስጥ 4,000 የሚሆኑት ሲሞቱ፣ ይህ የማኅጸን ነቀርሳ ተጠቂ ቁጥር ከብሔራዊው አማካይ መጠን በላይ በዲሲ ከፍ ብሎ ይገኛል።

ለ HPV በሽታ የሚሰጥ የመከላከያ ክትባት ሕይወት የሌለው (ሕያው ያልሆነ) ዐይነት ሆኖ ነገር ግን እንዲንሰራራ በማድረግ አራት ዋና የ HPV ተዋህስያንን ዐይነቶች የመከላከል ችሎታ አለው። እነዚህም 70% ወይም እጅ ያህል የማኅጸን ነቀርሳ የሚያስከትሉትን ሁለት ዐይነት እና እንዲሁም ወደ 90% ወይም እጅ የአባለ ዘር እከክ (genital warts) የሚያመጡትን ሁለት ዐይነት HPV ያካትታል። የHPV ክትባት አብዛኛውን የአባለዘር እከክ (genital warts) እና አብዛኛውን የማኅጸን ነቀርሳ (cervical cancer) ለመከላከል ያስችላል።

እነዚህ መከላከያዎች በሽታዎችን ለረጅም ጊዜ እንዲከላከሉ የሚጠበቁ ናቸው። ይሁን እንጂ የተከተቡ ሴቶችም ቢሆን የማኅጽን ነቀርሳ የማጣሪያ ምርመራ ማድረግ ይኖርባቸዋል። ይህም የሆነበት ምክንያት ክትባቱ የማኅጸን ነቀርሳ (cervical cancer) የሚያስከትሉን የ HPV ሁሉንም ጠንቆች የማይከላከል በመሆኑ ነው።

የ HPV ክትባት፣ የእድሜ ክልላቸው ከ 11-12 ዓመት ለሆኑ ታዳጊ ልጆች በየጊዜው የሚታዘዝ ሲሆን፣ እስከ 9 ዓመት እድሜ ላላቸው ልጆችም ቢሆን ሊታዘዝ ይችላል። ለወንድ ልጆች እና ሴት ልጆች፣ በመጀመሪያ የግብረ ሥጋ ንክክ ከመጀመራቸው በፊት፣ ለ HPV ተውሳክ ተጋልጠው ያልነበሩ በመሆናቸው የመጀመሪያቸው ከሆነው የግብረ ሥጋ ግንኙነታቸው በፊት የ HPV ክትባት ወስዶ መገኘት እጅግ ጠቃሚ ነው። ክትባቱ ከሁሉም ዐይነት የ HPV በሽታ ሳይሆን – ከጥቂት ዐይነት ይከላከላል። ሆኖም አንድ ወንድ ወይም ሴት ልጅ በ HPV ተውሳኮች በአንዱ ቀድሞውኑ ተይዘው የነበሩ ከሆነ ክትባቱ በሽታውን አያድንም። ይሁን እንጂ አሁንም ቢሆን በ HPV በሽታ የተያዙ ወንድ ልጆች እና ሴት ልጆች እንዲከተቡ ይመከራሉ። በተጨማሪም፣ የ HPV ክትባት በሴት ልጆች ላይ ከብልት ነቀርሳ በሽታ እና ሴት ልጅ ብልት ውጫዊው አካል ነቀርሳ (vulvar cancer) የሚከላከ ሲሆን፣ በሴቶች እና በወንዶች ልጆች ለሁለቱም ደግሞ ከአባለ ዘር እከክ (genital warts) እና የፊንጢጣ (anal cancer) ነቀርሳን ይከላከላል።

ክትባቱ በተጨማሪ እድሜአቸው ከ 13-26 ዓመት ለሆናቸው ሴቶች እና እንዲሁም ከ 13-21 እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ወንዶች (ወይም በአንዳንድ ሁኔታ እስከ 26 ዓመት የሞላቸው) እና ከዚህ በፊት ወጣት በነበሩበት ዘመን ክትባቱን ሳይወስዱ የቀሩ ሁሉ እንዲወ ስዱ ይጠበቃል። ይህም ክትባት፣ አስፈላጊ ከሆኑ ከሌሎች ክትባቶች ጋር ሊሰጥ ይችላል።

የ HPV ክትባት እንደ ሦስት ተከታታይ ልከ መጠን ይሰጣል።
 1ኛ ልከ መጠን፤ አሁን
 2ተኛ ልከ መጠን፤ ከ 1ኛ ልከ መጠን ሁለት ወራት በኋላ
 3ተኛ ልከ መጠን፤ ከ 1ኛ ልከ መጠን ስድስት ወራት በኋላ

ለሻጋታ ወይም ለእርሾ (yeast)፣ ለሕይወት አስጊ የሆነ አለርጂ ፣ ወይም ነፍሰ ጡር የሆኑ፣ ከመካከለኛ እስከ አስከፊ የሆነ በሽታ ያለባቸው ሁሉ መከተብ የለባቸውም። ክትባቱ የሚያስከትለው ጠንቅ አብዛኛውን ጊዜ ማሳከክን፣ ሕመምን፣ መርፌ በተወጉበት አካባቢ ላይ የሰውነት መቅላትን የመሳሰሉ ከዝቅተኛ እስከ መካከለኛ ትኩሳት ያስከትላል።

በነአቶ መላኩ ፈንታ የክስ መዝገብ 28 ክሶች እንዲሻሻሉ ፍርድ ቤት በየነ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የቀድሞውን የጉምሩክ ባለስልጣን የእነ አቶ መላኩ ፈንታን የሙስና ክስ የሚመለከተው ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት በተጠርጣሪዎቹ የክስ መዝገቦች ክስ መቃወሚያ ላይ ዛሬ ብይን አስተላለፈ። ከአዲስ አበባ ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች እንደሚያሳዩት በዛሬው ዕለት የተሰየመው ችሎት ከሁለት ሳምንት በፊት ከሳሽ አቃቢ ህግና የተከሳሽ ጠበቆች ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያና ምላሽ ተንተርሶ ግልጽ ባልሆኑና ማብራሪያ በሚፈለጉ ጉዳዮች ላይ አከራክሮ ብይን ለመስጠት የነበረ ሲሆን በዚህም መሠረት 28 ክሶች እንዲሻሻሉ ፍርድ ቤቱ አዟል።
Melaku-Fenta-and-Gebrewahid-Woldegiorgis
በዛሬው እለት የተሰየመው ፍርድ ቤት እንዳለው እነ መላኩ ፈንታን ጨምሮ ከፍተኛ ባለስልጣናትና ነጋዴዎች የሚገኙባቸው ሶስት መዝገቦች ውስጥ ከተካተቱ 138 ክሶች መካከል 28 የሚሆኑት እንዲሻሻሉ የተወሰነ ሲሆን በ3ኛው የክስ መዝገብ ከጉቦ ጋር የተያያዙ ክሶች ከዋናው መዝገብ እንዲነጠሉም ተወስኗል።

የቀድሞው የጉምሩክ ባለስልጣንት አቶ መላኩ ፈንታ “ከገቢ በላይ ሃብት ማካበት” በሚል የተመሰረተባቸውን ክስ በተመለከተም በመንግስት ከተቀጠሩ ወዲህ ያላቸው ገቢና ሌላም ገቢ ካላቸው ተዘርዝሮ እንዲቀርብ ፍርድቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቶ ሰኔ 3 ቀን 2006 ዓ.ም የተሻሻለውን ክስ ለማየት ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ለዘ-ሐበሻ የደረሱት መረጃዎች ጠቁመዋል።

በማኅበረ ቅዱሳን ጉዳይ፤ የሲኖዶስ ጉባኤ በፓትርያርኩና ጳጳሳቱ ፍጥጫ ተቋጨ – (አዲስ አድማስ ጋዜጣ)

$
0
0

ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንደዘገበው፦

ጳጳሳት የፓትርያርኩን የማኅበረ ቅዱሳን ደንብ ማሻሻያ ቅድመ ኹኔታ አልተቀበሉትም

‹‹ቅድመ ኹኔታው የማኅበሩን አገልግሎት የሚያቀጭጭና በሒደትም የሚያስቆም ነው›› /ታዛቢዎች/

የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅን እንደ አንድ አጀንዳ የያዘው የዘንድሮው የሲኖዶሱ የርክበ ካህናት ጉባኤ ከረቂቁ ጋር በተያያዘ በፓትርያርኩና በሊቃነ ጳጳሳቱ መካከል በተፈጠረ ፍጥጫ መጠናቀቁ ተገለጸ፡፡
የፍጥጫው መንሥኤ፣ በቅዱስ ሲኖዶሱ የተሠየመው የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደርያ ደንብ አጥኚ ኮሚቴ ያዘጋጀው የማሻሻያ ረቂቅ በዝርዝር ከመታየቱ አስቀድሞ ፓትርያርኩ ለውይይቱ እንደ ቅድመ ኹኔታ ያቀረቧቸው ነጥቦች በአብዛኛው የጉባኤው አባላት የገጠመው ተቃውሞ እንደኾነ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
የቅ/ሲኖዶሱን ስብሰባ በርእሰ ጉባኤነት የሚመሩት ፓትርያርኩ፤ በአጀንዳው ላይ የሚካሔደውን ውይይት ቀጣይነት ይወስናል በሚል ካቀረቧቸው ቅድመ ኹኔታዎች ውስጥ÷ ለአጥኚ ኮሚቴው መመሪያ የሰጡባቸው ‹‹ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችና ግዴታዎች›› አንድም ሳይቀነሱ በደንቡ እንዲካተቱና ረቂቁ ሕገ ቤተ ክርስቲያኑ ከጸደቀ በኋላ እንዲታይ የሚሉ እንደሚገኙበት ተመልክቷል፡፡
Holy sinod addis ababa
ፓትርያርኩ በቅድመ ኹኔታ አስቀምጠዋቸዋል በተባሉት ነጥቦች ስምምነት ላይ ከተደረሰ ስብሰባው ሊቀጥል እንደሚችል በመጥቀስ፣ ኃይለ ቃልም ተማኅፅኖም በተቀላቀለበት አኳኋን መጠየቃቸው ተዘግቧል፡፡
ይኹንና የሚበዙት ሊቃነ ጳጳሳት በቀጥታ እንደተቃወሟቸው፣ የተቀሩትም ድጋፍ ከመስጠት እንደተቆጠቡ ታውቋል፡፡ ፍጥጫው ቀጥሎ አቡነ ማትያስ ‹‹አቋሜ ይኽው ነው፤›› በሚል አጀንዳውን መዝጋታቸውን ሲያስታውቁም፣ ‹‹የማኅበረ ቅዱሳን ጉዳይ እንዲህ ተብሎ የሚተው አይደለም፤›› በሚል ከኹሉም ሊቃነ ጳጳሳት ጠንካራ ተቃውሞ እንደገጠማቸው ምንጮች ይገልፃሉ፡፡

የቅ/ሲኖዶሱ መደበኛ ስብሰባ የሚካሔደው ምልዓተ ጉባኤው ከጅምሩ ተስማምቶ ባጸደቃቸው የመነጋገርያ አጀንዳዎች መሠረት እንደኾነ በሊቃነ ጳጳሳቱ ተቃውሞ ተጠቅሷል፡፡

የማኅበሩ የመተዳደርያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅ እንዲቀርብ ከታዘዘበት ከጥቅምት 2005 ዓ.ም. ጀምሮ እየተንከባለለ ለኹለት ዓመታት መዘግየቱን ሊቃነ ጳጳሳቱ አስታውሰው፣ የተጓተተው አጀንዳ ‹‹የማኅበሩን አገልግሎት ያቀጭጫሉ፣ በሒደትም ያስቆማሉ›› በሚል በተተቹት የፓትርያርኩ ቅድመ ኹኔታዎች ሊዘጋ እንደማይችልና ተጨማሪ ጊዜ ሳይወስድ ቅ/ሲኖዶሱ ሊወያይበት እንደሚገባ በአጽንዖት በመናገራቸው፣ ጉዳዩ ሳይቋጭ ለቀጣዩ ቀን በይደር ተላልፏል፡፡

አጀንዳው ሰኞ፣ ግንቦት 18 ቀን 2006 ዓ.ም. ጥዋት መታየት ሲጀምር፣ አጥኚ ኮሚቴው በ37 አንቀጾችና በ34 ገጾች አሻሽሎ ያዘጋጀው የማኅበሩ መተዳደርያ ደንብና የኮሚቴው ቃለ ጉባኤ በንባብ መሰማቱም ታውቋል፡፡ ፓትርያርኩ ‹‹ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችና ግዴታዎች›› በሚል ራሱን በቻለ ርእስ በደንቡ እንዲካተት ለአጥኚ ኮሚቴው ጥብቅ መመሪያ የሰጡበት ባለ24 አንቀጽ ሰነድም አብሮ እንዲነበብላቸው መጠየቃቸው የመጀመሪያው ቀን የፍጥጫ መነሻ እንደነበር ታውቋል፡፡

በ24 አንቀጾችና በአምስት ገጾች የተዘረዘሩት የፓትርያርኩ ልዩ ልዩ ድንጋጌዎችና ግዴታዎች÷ በአባላቱ በጎ ፈቃድ ተቋቁሞ ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማበርከት ላይ የሚገኘውን ማኅበር፤ ከሕገ ተፈጥሮው ውጭ የሚያደርግ፣ በቅ/ሲኖዶሱ ፈቃድ ከሚመራበት ደንብ በተፃራሪ ተቋማዊ ህልውናውን፣ የአመራር ምርጫውን፣ የአባላት አያያዙንና የሥራ ቦታውን ለውጭ ተጽዕኖ አሳልፎ የሚሰጥና አጣብቂኝ ውስጥ የሚያስገባ፣ በአርኣያነት የሚጠቀሰውን የፋይናንስ አሠራሩን ወደ ኋላ የሚጎትት መኾኑን እንደተረዱ ያብራሩ አንድ የቅ/ሲኖዶሱ አባል፣ ‹‹ቀጣዩ ቀንም የከበደ ነገር ይዞ እንደሚመጣ ግልጽ ነበር፤›› ይላሉ፡፡
በይደር የተያዘው አጀንዳ በቀጣዩ ቀን ማክሰኞ ጥዋት ተጀምሮ ለግማሽ ቀን የቀጠለ ቢኾንም ፓትርያርኩና ሊቃነ ጳጳሳቱ የመተዳደርያ ደንብ ማሻሻያውን በዝርዝር ለመመልከት የሚያስችል ስምምነት ላይ ለመድረስ እንዳልቻሉ ታውቋል፡፡

‹‹ፓትርያርኩ በቅድመ ኹኔታ ያስቀመጧቸውን ነጥቦችና በአጀንዳው ቀጣይነት ላይ የያዙትን አቋም አልቀየሩም፤ ሊቃነ ጳጳሳቱም ባጸደቅነው አጀንዳ መሠረት ቅድሚያ ሰጥተን መነጋገር ያለብን የሠየምነው አጥኚ ኮሚቴ አዘጋጅቶ ባቀረበው ረቂቅ ላይ ነው፤ መካተት ያለበት ነገር ካለም ማኅበሩን በሚያሠራ መልኩ እያገናዘብን በሒደት እናየዋለን እንጂ አጀንዳው በቅድመ ኹኔታ መታሰር የለበትም በሚል ለማስረዳት ጣሩ፤ በመጨረሻም ፓትርያርኩ “እንግዲያውስ ስብሰባውን ለመምራት አልችልም” በማለታቸው የስብሰባው መቋጫ ኾኗል፤›› ይላሉ- ሒደቱን ለአዲስ አድማስ የገለጹ የስብሰባው ምንጮች፡፡
የማኅበሩ ደንብ በመጀመሪያ ረድፍ ከሰፈሩት የቅ/ሲኖዶሱ መነጋገርያ ነጥቦች አንዱ እንደነበር ያስተዋሉ ሌሎች የስብሰባው ተከታታዮች በበኩላቸው፤ አጀንዳው ከቅደም ተከተሉ ወጥቶ እየተገፋ በመጨረሻ መነሣቱ በፓትርያርኩና በሊቃነ ጳጳሳቱ መካከል ይህ ዓይነቱ አለመግባባት ሊነሣ እንደሚችል ጠቋሚ ነበር ብለዋል፡፡

ተከታታዮቹ አክለውም፣ ፓትርያርኩ ስብሰባውን ለመምራት ፈቃደኛ ባይኾኑም በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ በተደነገገው የቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ ሥነ ሥርዓት መሠረት፣ ምልዓተ ጉባኤው በማኅበሩ መተዳደርያ ደንብ ማሻሻያዎች ላይ የጀመረውን ውይይት ቀጥሎ ውሳኔ ለማሳለፍ የሚችልባቸው አግባቦች እንደነበሩ ገልጸው፣ ቅ/ሲኖዶሱ በግለጫው የመጨረሻው አጀንዳው ባደረገው የማኅበሩ ደንብ ላይ “ውይይት ተደርጎበታል” ከማለት በስተቀር ስብሰባውን የቋጨበት አኳኋን ያልተለመደና አደናጋሪ ነው ብለዋል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን የዘመኑን ኦርቶዶክሳዊ ትውልድ አደራጅቶ ማንነቱን የሚያውቅበትንና በግብረ ገብ የሚታነፅበትን ትምህርተ ሃይማኖት ከማስተማር ባሻገር፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ተቋማት አገልግሎታቸውን በብቃት የሚወጡበትን ኹለገብ ሞያዊ ድጋፍ የመስጠት ሓላፊነት እንዳለበት በደንብ አጥኚ ኮሚቴው ማሻሻያ ረቂቅ ላይ መስፈሩ ታውቋል፡፡

ይኹንና ‹‹ጥበቃና ጥንቃቄ›› በሚል ፓትርያርኩ እንደ መመሪያ ያቀረቧቸው ድንጋጌዎችና ግዴታዎች እንዲሁም ከልዩ ጽ/ቤታቸው ማኅበሩን አስመልክቶ በየጊዜው የሚወጡ መመሪያዎች የማኅበሩን አገልግሎት የማቀጨጭ፣ በሒደትም አዳክሞ የማስቆም ውጤት ሊኖራቸው እንደሚችል ታዛቢዎች ያስረዳሉ፡፡

የማኅበሩ መተዳደርያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅ፣ ቅ/ሲኖዶሱ የማኅበሩ ደንብ እንዲሻሻል ግንቦት 14 ቀን 2004 ዓ.ም. ባካሔደው ስብሰባ÷ ማኅበሩ ከጊዜው ጋር የሚሔድ፣ አገልግሎቱና አደረጃጀቱ የደረሰበትን ስፋትና ዕድገት የሚመጥን፣ ለቤተ ክርስቲያን ኹለንተናዊ ልማት የሚጠቅም ድርጅታዊ መዋቅር እንደሚያስፈልገው ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት አምስት ሊቃነ ጳጳሳት፣ ገለልተኛ የሕግ ባለሞያዎችና የማኅበሩ አባላት በታከሉበት አጥኚ ኮሚቴ የጋራ ጥናት የተዘጋጀ መኾኑ ተመልክቷል፡፡
በግንቦት ወር 1984 ዓ.ም. በበጎ ፈቃድ በተሰበሰቡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የተመሠረተው ማኅበሩ፤ እየተመራ ያለው ቅ/ሲኖዶስ በ1994 ዓ.ም. ለሦስተኛ ጊዜ አሻሽሎ በሰጠው መተዳደርያ ደንብ ሲኾን አሁን የተሻሻለው ረቂቅ ተመርምሮ ባለመጽደቁ በነባሩ ደንብ እየተመራ ለመቀጠል እንደሚገደድ ተመልክቷል፡፡

Sport: የማን.ዩናይትዱ ማታ አሻግሮ እየተመለከተ ነው

$
0
0

ዓመቱ ለማንቸስተር ዩናይትድ አስከፊ ነበር፡፡ ሪከርድ በሆነ ዋጋ ዩናይትድን ለተቀላቀለው ሁዋን ማታም ቢሆን የተሻለ አልነበረም፡፡ ስፔናዊው ፕሌይሜከር የቻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊ ነበር፡፡ ለሁለቱ ተከታታይ ዓመታትም የቼልሲ ምርጥ ተጨዋችነት ክብርን ተቀዳጅቷል፡፡ ጆዜ ሞውሪንሆ ግን በዋናው ቡድን የመሰለፍ ዕድል ነፈጉት፡፡ በኋላ ላይም ውጤቱን እያሽቆለቆለ ለነበረው ዩናይትድ ተሸጠ፡፡ በዚህም ምክንያት ማታ ገና ከአሁኑ መጪውን የውድድር ዘመን አሻግሮ መመልከት ጀምሯል፡፡ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ዩናይትድ በአውሮፓ መድረክ አለመሳተፉ በሊጉ ከአናት የመቀመጥ ዕድሉን ያሰፋዋል ብሎም ያምናል፡፡ ክለቡንም ሆነ እርሱን መከራ እንደመከራቸውም ያስባል፡፡ ‹‹በቼልሲ ያለፍኩበት ሁኔታ ከዚህ ቀደም በተጨዋችነት ዘመኔ አጋጥሞኝ የማያውቅ ነገር ነው፡፡ በቋሚነት አልሰለፍም ነበር፡፡ ነገር ግን ይበልጥ ጠንካራ እንዳደረገኝ አስባለሁ፡፡ በመከራ ውስጥ ስታልፍ በራስህ ያለህን እምነት ልታጣ ትችላለህ፡፡ እኔ ግን በልበ ሙሉነቴ ፀናሁ፡፡ ዓላማዎቼንም አልሳትኩም›› በማለት በሰማያዊዎቹ ቤት ያጋጠመውን ያስታውሳል፡፡

ሊቨርል በዚህ የውድድር ዘመን ተነቃቅቷል፡፡ ወጥ አቋምም አበርክቷል፡፡ ለዚህ ስኬት በዋናነት ከሚጠቀሱ ምክንያቶች አንዱ በአውሮፓ መድረክ ተሳትፎ አለማድረጉ ነው፡፡ ይህን የተገነዘበው ማታ ዩናይትድ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን የሊቨርፑልን ገድል ይደግማል ብሎ ያምናል፡፡ ‹‹እርግጥ በቻምፒዮንስ ሊግ ብጫወት እመርጥ ነበር፡፡ ያ አለመሆኑ ግን በሊጉ የተሻለ ዕድል እንዲኖር ያደርጋል፡፡ ሊቨርልን እንደምሳሌ መውሰድ ይቻላል፡፡ በቻምፒዮንስ ሊግ ባለመጫወቱ እስከ ውድድር ዘመኑ ፍፃሜ ድረስ ለዋንጫ በሚደረገው ትንቅንቅ ዋነኛ ተዋናይ መሆን ችሏል›› ሲል ሃሳቡን በምሳሌ ያጠናክራል፡፡
mata manchester united
ማታ ቻምፒዮንስ ሊግን አሸንፏል፡፡ ይህንንም የሚያረጋግጥ ሜዳሊያ በእጁ ላይ ይገኛል፡፡ በሙኒክ የቻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ዲዲዬ ድሮግባ በግንባሩ ገጭቶ ላስቆጠራት ጎል ኳሷን አመቻችቶ ያቀበለውም እርሱ ነበር፡፡ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ወደዚህ ዝነኛ ውድድር ዳግም ለመመለስ የሚያደርጉትን ጥረት የሚመራው ማን እንደሆነ ግን በእርግጠንነት መናገር አይቻልም፡፡

በልንቱ እንደ አርአያ ይመለከተው ከነበረው ሪያን ጊግስ ጋር የጠበቀ ትስስር እንዳላቸው ግልፅ ነው፡፡ ‹‹አርአያ የሆኑህን ሰዎች ልታገኛቸው አይገባም›› የሚለው ያረጀ ያፈጀ አባባል በዚህ አውድ የሚሰራ አይመስልም፡፡ ‹‹ክለቡን እንደተቀላቀልኩ በልጅነቴ የእኔ አርአያ እርሱ እንደነበር ነገርኩት፡፡ እርሱም ወደዚህ በመምጣትህ ደስ ብሎኛል፡፡ በመጠኑም ቢሆን ግን ቅሬታ አለብኝ፡፡ ምክንያቱም አንተ በዚህ በመገኘትህ እኔ በክለቡ ሁለተኛው ምርጥ የግራ እግር ተጨዋች ሆንኩ አለኝ፡፡ ያ ሊሆን እደማይችል ነገርኩት፡፡ በታዳጊነቱ በቅርበት እከታተለው የነበረ ተጨዋች ነው፡፡ ኳስን የሚቆጣጠርበትን እና የሚገፋበትን መንገድ እወድደዋለሁ፡፡ እውነተኛ የግራ እግር የክንፍ ተጨዋች ነው፡፡ ፈጣን ነው፡፡ አንድ ለአንድ በምትገናኝበት ወቅት ደግሞ ለማቆም ትቸገራለህ፡፡ በዚያ ላይ ጎሎችን ያስቆጥራ፡፡ አሁን ግን የዕጣ ፈንታ ጉዳይ ሆኖ የቡድን አጋሬ እና አሰልጣኜ ሆኗል›› ሲል ለዌልሳዊው ያለውን ክብር ይገልፃል፡፡
ማታ ጊግስ በዩናይትድ አሰልጣኝነት ብዙም እንደማይቆይ ያውቃል፡፡ መጪው ጊዜ ይዞት የሚመጣውንም ነገር በመጠባበቅ ላይ ነው፡፡ ስለ ሉዊ ቫን ሃል ሲጠየቅ ‹‹ከእርሱ ጋር ተገናኝቼ አላውቅም፡፡ ምን አይነት ታሪክ እንዳለው ግን አውቃለሁ፡፡ ስላሸነፋቸው ዋንጫዎች እና የሆላንድ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኛችን ስላልሆነ ሰው ማውራት ተገቢ አይመስለኝም›› ሲል ምላሽ ይሰጣል፡፡
ሆላንዳዊው ጊግስን ተክተው የኦልድ ትራፎርዱን ክለብ የሚረከቡ ከሆነ በሶስት የውድድር ዘመን ማታን ያሰለጠኑ ሰባተኛው አሰልጣን ይሆናሉ፡፡ ለዚህ ደግሞ በዋናነት የሚጠቀሱት ትዕግስት አልባ የሆነው የእንግሊዝ እግርኳስ እና ለትንሿ ነገር የተጋነነ ምላሽ በመስጠት የሚታወቁት የስፔን ክለቦች ፕሬዝዳንቶች ናቸው፡፡

ታዲያ ማታ እነዚህን አሰልጣኞች እንዴት ያነፃፅራቸዋል? ‹‹ወደ እንግሊዝ ያመጣኝ አንድሬ ቪያስ ቦአስ ነው፡፡ በእኔ ላይም ትልቅ እምነት ነበረው፡፡ ወጣት ነው፡፡ ትልቅ ራዕይም ነበረው፡፡ ቡድኑ ማራኪ እና አሸናፊ የሆነ እግርኳስን እንዲጫወት ይፈልግ ነበር፡፡ ሁልጊዜም ቢሆን ለእርሱ ክብር አለኝ፡፡ ሮቤርቶ ዲ ማቴዮ በመጠኑ ከጊግስ ጋር ይመሳሰላል፡፡ የቀድሞ ተጨዋች እና ረዳት አሰልጣኝ ነበር፡፡ ቪያስ ቦአስ ሲለቀቅ እርሱ ክለቡን ተረከበ፡፡ ታላቅ ስኬትም አስመዘገበ፡፡ የቻምፒዮንስ ሊግ እና የኤፍኤ ካፕ ዋንጫዎችን ማንሳት ቻልን፡፡ ከእኔ ጋርም ሆነ ከተቀሩት የቡድኑ አባላት ጋር መልካም ግንኙነት ነበረው፡፡ ህብረት እና ቁርጠኝነት እንዲኖረንም አድርጓል፡፡

‹‹ከዚያም ከራፋኤል ቤኒቴዝ ጋር በመሆን የዩሮፓ ሊግን አሸነፍን፡፡ በቀደመው ታሪኩ የተነሳ መጀመሪያ አካባቢ ሁኔታዎች አስቸጋሪ ሆነውበት ነበር፡፡ ነገር ግን ያህንን ሁሉ ተቋቁሞ መልካም ስራ እንደሰራ አስባለሁ፡፡ ፕሮፌሽናል ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ክለቡ ከዚህ ቀደም አሸንፎት የማያውቀውን ዋንጫ እንዲያነሳ አስቻለ›› በማለት አብሯቸው ውጤታማ መሆን ስለቻላቸው አሰልጣኞች በአድናቆት ይናገራል፡፡

ዘንድሮ ደግሞ ጆዜ ሞውሪንሆን ዳግም ሰማያዊዎቹን ተቀላቀሉ፡፡ ነገር ግን ከማታ ጋር ሊግባቡ አልቻሉም፡፡ ለምን? ወሳኙ ነገር ግንኙነት አለመመስረታቸው ይመስላል፡፡ ነገር ግን እርሱም ቢሆን የአለመግባባቱ ምልክት እንጂ ምክንያት ሊሆን እንደማይችል ግልፅ ነው፡፡ ለምን ከቋሚ አሰላለፍ ውጪ እንዳደረጉት ሞውሪንሆን ጠይቋቸው ያውቅ እንደሆነ ሲጠየቅ በፍፁም፡፡ አስፈላጊ መስሎም አልታየኝም ሲል ምላሽ ይሰጣል፡፡ ሞውሪንሆስ ቢሆኑ ለምን በቡድኑ ውስጥ ቦታ እንዳጣ አብራርተውለት ይሆን? በጭራሽ በማለት ስፔናዊው አጭር መልስ ይሰጣል፡፡
በመጨረሻም ቼልሲ እና ዩናይትድ ከተደራደሩ በኋላ በጃንዋሪ 25 በሄሊኮፕተር ካሪንግተን ደረሰ፡፡ ‹‹ለቼልሲ ምስጋናዬን ማቅረብ እፈልጋለሁ፡፡ ዳይሬክተሮቹ፣ ባለቤቱ እና ደጋፊዎቹ ከመጀመሪያዋ ቀን አንስቶ እስከ መጨረሻዋ ዕለት ለእኔ መልካሞች ነበሩ፡፡ መልካሙን ሁሉ እመኝላቸዋለሁ፡፡ በዚያ በርካታ ወዳጆች አሉኝ፡፡ ሴዛር አዝፒሊኩኤታ፣ ፈርናንዶ ቶሬስ፣ ዴቪድ ልዊዝ እና ኦስካር ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ከላምፓርድ እና ቴሪ ጋርም በብዛት እንነጋገራለን፡፡ ወደ ሶስት ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ አብሬያቸው ነበርኩ፡፡ በመሆኑም በጎ በጎው ነገር እንዲገጥማቸው እመኛለሁ›› ሲል የቀድሞ ክለቡን በመልካም ያነሳል፡፡

ክለቡን ለቅቆ በሄደበት ወቅት ለደጋፊዎች በፃፈው የስንብት እና የምስጋና ደብዳቤም ኩራት ይሰማዋል፡፡ ‹‹ያንን ያደረግኩት ገፅታዬን ለመገንባት አይደለም፡፡ በጥሩ ሁኔታ ሲንከባከቡኝ ስለነበሩ ደጋፊዎች እና ስለ ቼልሲ የሚሰማኝን መግለፅ በመፈለጌ ከልብ የመነጨ ነበር›› በማለት ያንን ለማድረግ የተነሳሳበትን ምክንያት ይገልፃል፡፡

እንደህ በይፋ ለባላንጣ ክለብ ደጋፊዎች ያለውን ፍቅር መግፁ ከቀያይ ሰይጣናቱ ደጋፊዎች ጋር ሊያቃቅረው ይችላል ተብሎ ሊታሰብ ይችላል፡፡ ነገር ግን ይህ ድርጊቱ የሚያሳየው የሰውነቱን ልክ ነው፡፡ ከቀዮቹ ጋር ዋንጫዎችን ለማሸነፍ ጓጉቷል፡፡ የሚሰለፍበትን ቦታ አስመልክቶ ተንታኞች ብዙ ማውራታቸውንም የወደደው አይመስልም፡፡

‹‹እራሴን የቀኝ ክፍን ተጨዋች አድርጌ እንደማልቆጥር የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን በግራ እግሬ ወደ ውስጥ ሰብሬ የምገባበትን ዕድል ያጎናፅፈኛል፡፡ ቫሌንሲያ በነበርኩበት ወቅት በግራ መስመር ተጫውቼ አውቃለሁ፡፡ በብሔራዊ ቡድኑም እንደዚው ምርጥ ብቃቴን የማሳየው ግን ከአጥቂዎቼ ጀርባ ስሰለፍ ነው፡፡ ነገር ግን በሌሎቹም ሁለት ቦታዎችም መልካም እንቅስቃሴ እንደማደርግ አስባለሁ፡፡

ማታ ከዩናይትድ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴ ሂያ ጋር ሆኖ የዓለም ወጣቶች ሻምፒዮናን አሸንፏል፡፡ የዩናይትድ የዓመቱ ምርጥ ተጨዋች ተብሎ የተመረጠው ዴ ሂያ ከኦልድት ትራፎርድ ታላላቅ ተጨዋቾች ተርታ ሊያሰልፈው የሚችል የአዕምሮ ዝግጅት እንዳለውም ያምናል፡፡ ‹‹በራሱ ከፍተኛ እምነት አለው፡፡ ያ ደግሞ እጅግ አስፈላጊ ፀጋ ነው፡፡ ምንም ነገር ተፅዕኖ እንዲያሳድርበት አይፈቅድም፡፡ ስህተት በሚፈፅምበት ወቅት ማጥፋቱን ይገነዘባል፡፡ ነገር ግን ስህተቱን በማምሰልሰል ለዳግም ጥፋት አይዳረግም፡፡ ስህተቱን የሚጠቀመው ሌላ ስህተት ላለመፈፀም እንደመማሪያ አድርጎ ነው፡፡ በዚያ ላይ በጣም የተረጋጋ ነው›› በማለት ለአገሩ ልጅ ምስክርነቱን ይሰጣል፡፡

‹‹በዚህ ዙሪያ ከጓደኞቼ ጋር ሳወራ የሊዮኔል ሜሲን ባህሪይን እንደ ምሳሌ ጠቀሱልኝ፡፡ ስለምንም ነገር የሚጨነቅ አይመስልም ሲሉም በአንድ አረፍተ ነገር ገለፁት፡፡ እውነታቸውን ነው፡፡ ጎሎችን ያስቆጥራል፡፡ ነገር ግን ምንም የተለየ ነገር እንዳልተፈጠረ ሁሉ ዘና ይላል፡፡ ምናልባት ያ መልካም ነገር ሳይሆን አይቀርም፡፡ የምትኖረው በከፍተኛ ጫና ውስጥ ነው፡፡ ሁልጊዜም ለራስህ ብለህ እንደሆንክ የምትነግረው ከሆነ በሆነ አጋጣሚ ስህተት ስትሰራ ለክፉ ጉዳት ትጋለጣለህ፡፡ በመሆኑም ሁሉም ነገር የተለመደ አድርጎ መመልከት ተገቢ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ይህም የታላላቅ ተጨዋቾች ብቃት እንደሆነ አስባለሁ››

በቀዩ የስፔን ማልያ እንዳደረጉት ሁሉ ዴ ሂያ እና ማታ በቀዩ የዩናይትድ ማልያ ያሸንፉ ይሆን? በራስ መተማመን ከኦልድ ትራፎርድ ርቋል፡፡ ከ13 ወራት በፊት ዩናይትድ በኦልድ ትራፎርድ 3-0 እየተመራ ቆይቶ 4-3 ማሸነፍ ይችል ነበር፡፡ አሁን ግን እንዲህ አይነቱን ውጤት ማስመዝገብ ተስኖታል፡፡ ቡድኑ በዚህ የውድድር ዘመን የጎደለው ዋነኛው ነገር በራስ መተማመን ነው፡፡ ነገር ግን ተጫዋቾቹም ሆነ ክለቡ እንደዚሁም ደጋፊዎች ይህንን የአሸናፊነት ስነ ልቦና መልሰው እንደሚያገኙት አምናለሁ፡፡ ይህ ክለብ ውጤት እንዲያስመዝግብ ከፍተኛ ጫና ይደረግበታል፡፡ በዚህ የውድድር ዘመን ዋንጫዎችን ማንሳት ካልቻልክ በቀጣዩ የውድድር ዘመን ስኬታማ እንድትሆን ይጠበቃል፡፡ በመጪው የውድድር ዘመን ይህን ባህላችንን አላማጣታችን ማስመስከር አለብን፡፡ ክለቡ ተወዳዳሪነቱን እና ማንነቱን እንዳላጣ ማሳያት ይኖርብናል በማለት ሃሳቡን ቋጭቷል፡፡


ሰበር ዜና -የአንድነት ፓርቲ እና መኢአድ ቅድመ ውህደት ፊርማ እሁድ ሰኔ 1 ቀን 2006 እንዲደረግ ተጠየቀ

$
0
0

በያሬድ አማረ

ፍኖተ ነፃነት

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በውህደት ጉዳይ ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ጋር ሲደረግ የነበረው ውይይት በመጠናቀቁና ሁለቱ ፓርቲዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ስምምነት ላይ በመድረሳቸው ምክንያት የቅድመ ውህደት ፊርማ ስነ-ስርዓት ሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲደረግ መወሰኑን የሚገልፅ ደብዳቤ ለአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) መላኩን የመኢአድ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነው ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡
እንደ ኃላፊው ገለፃ የቅድመ ውህደት ፊርማ ስነ-ስርዓቱን የሚያስፈፅሙ ከመኢአድ የተወከሉ የኮሚቴ አባላትንም ጭምር ያሳወቁ መሆኑንና በቀጣዩ ሳምንት የሚደረገው የቅድመ ውህደት ፊርማ ስነ-ስርዓትን በማካሔድ በአጭር ግዜ ውስጥ ሁለቱ ፓርቲዎች ወደ አንድ ውህድ ፓርቲነት እንደሚጠቃለሉና በቀጣይ ትግሉን በአንድነት ለመምራት የሚያስችል ሁኔታን ይፈጥራል ብለዋል፡፡

udJ&AEUP

የኢዴፓ ሕዝብ ግንኙነት በሴት ተማሪያቸው በስለት ተወጉ

$
0
0

በታምሩ ጽጌ

የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ወንድወሰን ተሾመ በአንዲት ሴት ተማሪያቸው በስለት ሦስት ቦታ ወግተው ኮሪያ ሆስፒታል መግባታቸውን ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡
news
አቶ ወንድወሰን በሴት ተማሪያቸው የተወጉት ግንቦት 22 ቀን 2006 ዓ.ም. ረፋዱ ላይ ገርጂ በሚገኘው ኢትዮ ፖርት ትምህርት ቤት ሲሆን፣ ደረታቸውን፣ ሆዳቸውንና ጭናቸውን መወጋታቸውን ምንጮቹ አረጋግጠዋል፡፡

ድርጊቱን ፈጽማለች የተባለችው ተጠርጣሪ ተማሪ፣ የ11ኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን፣ በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ ስትደርስ፣ የትምህርት ቤቱ መምህርና ዩኒት ሊደር የሆኑት አቶ ወንድወሰን፣ ቤተሰቧን እንዲጠሩላት ጠይቃቸው ወደ ምክትል ርዕሰ መምህር ክፍል ሄደው ስልክ በመደወል ላይ እያሉ መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡

በባህሪያቸው በትምህርት ቤቱ ተወዳጅ መምህር መሆናቸው የተገለጸው አቶ ወንድወሰን፣ በደረሰባቸው አደጋ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ቢሆንም፣ የኮሪያ ሆስፒታል ሠራተኞች ባደረጉላቸው የተፋጠነ ሕክምና ሕይወታቸው ሊተርፍ መቻሉንም ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ተጠርጣሪዋ ተማሪ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋሏንና ቦርሳዋ ሲፈተሽ ሦስት የስለት መሣሪያዎች መገኘቱንም ምንጮቹ አክለዋል፡፡

በ60ዎቹ የዕድሜ ክልል የሚገኙት የኢዴፓ ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነትና መምህር አቶ ወንድወሰን፣ በትምህርት ቤቱ ውስጥ ረጅም ጊዜ ያገለገሉ መሆኑን የጠቀሱት ምንጮቹ፣ ከሆሊሴቪየር ትምህርት ቤት በዚህ ዓመት በተዘዋወረች ተማሪ ድርጊቱ መፈጸሙ ግራ እንዳጋባቸው ተናግረዋል፡፡

በትምህርት ቤቱ የሚማሩ ተማሪዎች በሥነ ምግባር የታነጹ መሆናቸውን የትምህርት ቤቱ ማኅበረሰብ ሊመሰክር እንደሚችል የገለጹት ምንጮቹ፣ ጉዳዩ በፖሊስ የተያዘ በመሆኑ ስለተማሪዋና ከድርጊቱ ጀርባ ሌላም ነገር ካለ በቅርቡ ይፋ ይሆናል የሚል እምነት እንዳላቸው አክለዋል፡፡

ተማሪዋ በቁጥጥር ሥር መዋሏንና በገርጂ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ እንደምትገኘ፣ ከባድ የግድያ ሙከራ በመሆኑ ገና በምርምራ ላይ መሆኗን አንድ የፖሊስ አባል ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የኢትዮ ፖረንት ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ሲሳይ መርዕድን ማብራሪያ እንዲሰጡ ተጠይቀው ‹‹በስልክ መግለጫ አልሰጥም›› ብለዋል፡፡

የኢዴፓ ሊቀመንበር አቶ ሙሼ ሰሙ ስለ አቶ ወንድወሰን ጠይቀናቸው ድርጊቱን ባለመስማታቸው ተደናግጠው፣ ግንቦት 21 ቀን 2006 ዓ.ም. ተገናኝተው ግንቦት 24 ቀን 2006 ዓ.ም. የአባላትን ስብሰባ እንደሚመሩ ከመነጋገር ውጭ ምንም እንዳልሰሙ ተናግረዋል፡፡

ምንጭ፡ ሪፖርተር ጋዜጣ የእሁድ እትም

[የዞን 9 ጦማርያን ጉዳይ] ሦስተኛዋን ‹‹እሁድ››- በአራዳ ምድብ ችሎት –ዘገባ በጽዮን ግርማ

$
0
0

ችሎቱን ለመከታተል የመጡት ወጣቶች ከበፍቃዱ ኃይሉ ቤተሰቦች ጋራ እየተላቀሱ በጤና ጣቢያው በር በኩል ሲወጡ ፡፡ (ፎቶ በጽዮን ግርማ)

ችሎቱን ለመከታተል የመጡት ወጣቶች ከበፍቃዱ ኃይሉ ቤተሰቦች ጋራ እየተላቀሱ በጤና ጣቢያው በር በኩል ሲወጡ ፡፡
(ፎቶ በጽዮን ግርማ)


ጽዮን ግርማ
tsiongir@gmail.com

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ተጠርጣሪዎቹን እሁድ ለሚሰየም ተረኛ ችሎት መቅጠሩን የተለመደ አድርጎታል፡፡ ከቀናት በፊት በሦስቱ ብሎገሮች ላይ በተሰጠው የዐሥራ አራት ቀናት የጊዜ ቀጠሮ መሠረት የቀጠሮው ቀን ዛሬ ነበር፡፡ ዛሬ በዚህ ፍርድ ቤት ተገኝቼ የነበረውን ሁኔታ መከታተል ባልችልም ምንጮቼ የነገሩኝን ዝርዝር እንዲህ ጽፌዋለሁ፡፡

ጠዋት

የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰቦች እንደተለመደው የአራዳውን ምድብ ችሎት የጓሮ በር እያለፉ ወደ አሮጌው ፍርድ ቤት ግቢ መግባት የጀመሩት ጠዋት ሦስት ሰዓት ከመሙላቱ አስቀድሞ ነበር፡፡ አብዛኞቹ ከፍርድ ቤቱ ከፍ ብሎ በሚገኘው ማዕከላዊ ለሚገኙት እስረኛ ልጆቻቸው ቁርስ የማድረሻ ሰዓት ስለኾነ ዛሬም ከቁርስ መልስ ሰብሰብ ብለው ነበር ወደ ፍርድ ቤት ግቢ የገቡት፡፡

ፍርድ ቤቱ ሲደርሱ ግቢው በጸጥታ የተሞላ ነበር፡፡አንድም የተከፈተ የችሎት በር አልነበረም፣ግቢውን ከሚጠብቀው አንድ ፖሊስ በስተቀር ሌላ ሰው የለም፡፡ ጠባቂው ፖሊስ ‹‹ዋናዎቹ›› ሲመጡ አንድ ላይ መሰብሰባቸው አይቀርም ብሎ ይመስላል የሚገባውን ሰው በሙሉ አንድ ላይ እንዲሰበሰብ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ ሰዓቱ ረፈድ እያለ ሲመጣና ጸሐዩ ሲበረታ ግን ግቢው ውስጥ የቆመው ሰው ተበታትኖም ቢሆን ጥላ ፈልጎ እንዲቀመጥ ፈቀደ፡፡ የቀጠሮው ሰዓት እስኪደርስ ድረስ ሁሉም አመጣጡ እንደገጠመለት እየተቧደነ ባገኘው ነገር ላይ ተቀምጦ ፖሊስ ሊጠይቅ ይችላል ያሉትንና ፍርደ ቤቱ ሊሰጠው ስለሚችለው ትእዛዝ ግምታዊ መላምቱን እያስቀመጠ ጭንቀቱን በተስፋ ለማራገፍ ውይይቱን ቀጥሏል፡፡

‹‹ተጨማሪ ዐስራ አራት ቀን ሊጠይቁባቸው ይችሉ ይኾን?›› አንዱ ይጠይቃል፡፡ ‹‹የሽብር ተግባሩን ጠቅሰው ሃያ ስምንት ቀን ይጠይቁባቸዋል›› ሌላኛው ሰው አስተያየቱን ይሰጣል፡፡ ከተሰበሰቡት ሰዎች መካከል በፍርድ ቤት ጉዳዮች በቂ ልምድ ያለው አንድ የሕግ ባለሞያ፤‹‹መዝገቡ በጊዜ ቀጠሮ ላይ የሚገኝ ቢኾንም ባለፈው ቀጠሮ ፍርድ ቤቱ የፖሊስን የሽብር ተግባርና የሃያ ስምንት ቀን የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ ውድቅ ስላደረገው ዛሬ መልሶ እሱን ማንሳት አይቻልም ፖሊስ ጥያቄውን እንደገና ማቅረብ ቢፈልግ እንኳን በይግባኝ እንጂ መልሶ በዚህ ችሎት የሚያቀርብበት ሥርዓት አይኖርም፡፡›› በማለት ሞያዊ አስተያየቱን ሰጠ፡፡ የሕግ ባለሞያው የተቀመጠበትን ዙሪያ ከበው የተቀመጡት ወዳጅ ቤተሰቦች አስተያየቱን ሰምተው ‹‹ቢበዛ ፖሊስ ሊጠይቅ የሚችለው ዐሥራ አራት ቀን ነው፤እሱንም ቢኾን የሽብር ተግባሩን ሳያካትት በማለት›› ተስፋን ለራሳቸው ሰነቁ፡፡
ከዚህ ቀደም በነበሩት ቀጠሮዎች ችሎቱ ሲሰየምበት ከነበረው ሰዓት እያለፈ ሲሄድ ሁሉም ሰው ግራ ተጋብቶ የነበረ ቢኾንም አምስት ሰዓት ሊመላ ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩት አንድ ዕድሜው ከሃያ አራት የማይዘለው ጎርመስ ያለ ወጣት ወደ ፍርድ ቤቱ ግቢ ገብቶ ተራኛ ኾኖ መመደቡንና ነገር ግን ችሎቱም አለመከፈቱን የጽፈት ቤት ኃላፊም አለማግኘቱን በመግለጽ የፍርድ ቤቱ ሠራተኛ የሚመስለውን አንድ ሰው ጠየቀ፡፡ ለችሎት ጸሐፊዋ ስልክ ተደወለላት፡፡ እርሷ እስክትመጣም አስቀድሞ ተጠርጣሪዎቹን ይዞ ሊቀርብ ከመጣው መርማሪ ፖሊስ ጋር ወደ ውስጥ ዘለቀ፡፡
ሠላሳ ያህል ደቂቃዎች እንደተቆጠሩ እስረኞቹን ይዘው የመጡት ቁጦ (ከሌላው ጊዜ እጅግ የተለዩ) የፌደራል ፖሊሶች ወደ ግቢው ገብተው ተበታትኖ የቆመውን ቤተሰብ እንደተለመደው ሰብስበው በአንድ መስመር አቆሙት፡፡ ከፍርድ ቤቱ ግቢ ጀርባ ባለው መኪና ማቆሚያ ቦታ ለረጅም ሰዓት ተቀምጠው የቆዩትን ተጠርጣሪዎቹንም ይዘዋቸው ወደ ግቢው ገቡ፡፡ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች አቤል ዋበላና በፍቃዱ ኃይሉ እንደተለመደው በሰንሰለት ታስረው ገቡ፡፡ ማኅሌት ፋንታሁን እጆቿ በሰንሰለት ባይታሰሩም አንገቷን በሐዘን ቀብራ ነበር ወደ ግቢው የገባችው፡፡ አቤል የጠነከረ ቢመስልም የበፍቃዱ ዐይኖች መቅላት ለሊቱን በምርመራ ላይ ማደሩን ይጠቁማሉ፡፡

የበፍቃዱ ኃይሉ እናት በልጆቻቸው ተደግፈው ከዋናው ግቢ ከተባረሩ በኋላ የፍርድ ቤቱ ግቢ ጀርባ ካለው ጤና ጣቢያ በር በኩል ሲወጡ፡፡ (ፎቶ በጽዮን ግርማ)

የበፍቃዱ ኃይሉ እናት በልጆቻቸው ተደግፈው ከዋናው ግቢ ከተባረሩ በኋላ የፍርድ ቤቱ ግቢ ጀርባ ካለው ጤና ጣቢያ በር በኩል ሲወጡ፡፡
(ፎቶ በጽዮን ግርማ)


የእጆቻቸው ሰንሰለት ተፈቶ ችሎት ከገቡ በኋላ፤ከችሎት ውስጥ የሚወጣውን ምላሽ ለመጠበቅ ቤተሰብ ትንፋሹን ውጦ በቆመበት መጠባበቅ ጀመረ፡፡ እንደሌላው ጊዜ ቤተሰብ እንኳን እንዲገባ አልተፈቀደም ነበር፡፡ ዐሥር ደቂቃ እንኳን ሳይኾነው ለዘለፋ እና ለቁጣ የተዘጋጁ የሚመስሉ የፌደራል ፖሊሶች ወደ ተሰበሰበው ሰው ቀርበው ‹‹ግቢውን ለቃችሁ ውጡ እዚህ መቆም አይቻልም›› በማለት ማመናጨቅና መገፈታተር ጀመሩ፡፡ ‹‹ጠበቃው እስኪወጣ እንኳን እንጠብቅ የሚባለውን ከእርሱ ነው የምንሰማው›› ሲል ቤተሰብ ተማጸነ፡፡
አንዲት ሴት ፌደራል ፖሊስ እየተንደረደረች ወደ ተሰበሰበው ቀርባ ከፊት ያለውን ሰው መገፈታተር ጀመረች፡፡ ግፍተራው የደረሰባት የበፍቃዱ ኃይሉ እህት ግፍተራውን እየተከላከለች ፍርድ ቤት ግቢው ውስጥ ቆሞ የመጠበቅ መብት እንዳላት በመግለጽ ልታስረዳት ሞከረች፡፡ ፖሊሷ ተቆጣች እጅግም ተናደደች፤‹‹የምን መብት ነው ያለሽ፤ውጪ ብዬሻለሁ ውጪ፤አንተ ዱላውን አቀብለኝ›› የሥራ ባልደረባዋ ዱላውን እንዲያመጣላት ጠየቀች፡፡ ያሁሉ ሰው በተሰበሰበበት ዱላ ተቀብላ ለመማታት ተጋበዘች፡፡ የበፍቃዱ እናት ልጃቸውን ለመከላከል መሀል ገቡ ‹‹ዛሬ እናንተ ባለጊዜ ሆናችሁ ነው፤ፈጣሪ ፍርዱን ይሰጠናል›› እንባቸውን አረገፉት፡፡ ሌሎችም አገዟቸው፡፡ ቤተሰብ ተላቀሰ ፖሊሷ ግን ዱላዋን አቀባብላ ይበልጥ ተጠጋች ሰው ግቢውን ለቆ የማይወጣ ከኾነ ዱላው የማይቀርለት መኾኑን በሚገልጽ አኳኋን እያመናጨቀች አባረረች፡፡ ራሳቸውን ከፖሊሷ ዱላ መከላከል እንደማችሉ የገባቸው እናትና ልጅ እየተላቀሱ ተደጋግፈው ግቢውን ለቀው ወጡ ሌሎቹም ተከተሏቸው፡፡

ጠበቃው አቶ አመሐም ከችሎት ከወጣ በኋላ እንዳስረዱት ፖሊስ፤‹‹ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ በወንጀል በሥነ ሥርዓት ሕጉ አንቀጽ 59/2 መሰረት የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቀን በምርመራ ላይ ነበሩ፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ተጠርጣሪዎች ሚስጥራዊ በኾነ መንገድ በሕቡዕ በመደራጀት በሕጋዊ መንገድ ሥልጣን የያዘውን መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ ከሥልጣን ለማውረድ በማሰብ፣ ይህንንም ሐሳብ በውጭ አገር ከሚገኙ አሸባሪ ድርጅቶች ጋራ በመስማማትና አገሪቱን ለማተራመስ ትእዛዝ በመቀበል፣ትእዛዙን ለማሳካት የሚያስችላቸውን ገንዘብ በመቀበል፣እንዲሁም ስልጠና በመውሰድ በአገሪቱ ላይ ብጥብጥ ለማነሳሳትና ብጥብጡንም ለመምራት በመንቀሳቀስ የሽብር ተግባር ፈፅመዋል፡፡ በመኾኑም ይህን የሽብር ተግባር ለማጣራት እንዲረዳን በፀረ ሽብር ዐዋጁ ቁጥር 652/2001 አንቀፅ 28 መሰረት ተጨማሪ 28 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠን እንጠይቃለን››የሚለውን ቀደም ሲል አቅርቦት የነበረውን ማመልከቻ መልሶ አቀረበ፡፡ እኛም ይህ ማመልከቻ ተቀባይነት ሊያገኝ የማይችልበትን ምክንያት በመጥቀስ መከራከሪያችንን አቀረብን ዳኛው ፖሊስ የጠየቀውን የጊዜ ቀጠሮ ፈቀደ ብለዋል፡፡
ከዐሥራ አራት ቀናት በፊት በነበረው ቀጠሮ ችሎቱ ከተጠናቀቀ በኋላ ችሎቱን ለመታደም የመጣውን ሰው ፖሊስ ከግቢው ውጪ አቁሞት ነበር፡፡ ኾኖም ተጠርጣሪዎቹ በመኪና ተጭነው ሲወጡ ከበር ላይም ቢኾን እጁን እያውለበለበ፣ስማቸውን እየጠራና እያጨበጨበ ሸኝቷቸው ነበር፡፡ ዛሬ ግን ይህም አልነበረም ማንም ሰው የውጭው በር ላይ እንኳን እንዲቆም አልተፈቀደለትም፡፡

ምራቂ ወሬ

‹‹መዝገቡ በጊዜ ቀጠሮ ላይ የሚገኝ ቢኾንም ባለፈው ቀጠሮ ፍርድ ቤቱ የፖሊስን የሽብር ተግባርና የሃያ ስምንት ቀን የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ ውድቅ ስላደረገው ዛሬ መልሶ እሱን ማንሳት አይቻልም ፖሊስ ጥያቄውን እንደገና ማቅረብ ቢፈልግ እንኳን በይግባኝ እንጂ መልሶ በዚህ ችሎት የሚያቀርብበት ሥርዓት አይኖርም፡፡›› በማለት ሞያዊ አስተያየቱን ሰጠ፡፡ የሕግ ባለሞያው የተቀመጠበትን ዙሪያ ከበው የተቀመጡት ወዳጅ ቤተሰቦች አስተያየቱን ሰምተው ‹‹ቢበዛ ፖሊስ ሊጠይቅ የሚችለው ዐሥራ አራት ቀን ነው፤እሱንም ቢኾን የሽብር ተግባሩን ሳያካትት ነው ››በማለት ቀደም ሲል የሕግ አስተያየት ሰጥተው የነበሩት የሕግ ባለሞያ ችሎቱ ካለቀ በኋላ የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ ሲሰሙ የፍርድ ቤቶቹ አሠራር ፊት ለፊት ከሕጉ ጋር እየተጣረሰ መሄድ ግራ ሲያጋባቸው ታይተዋል፡፡ ‹‹ከዚህ በኋላ የሕግ ባለሞያዎች ትንታኔ ዋጋ የሚያጡበት ጊዜ በጣም እየቀረበም ነው›› ብለዋል፡፡

በሚኒሶታ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለአርቲስት ቴዎድሮስ ታደሰ ያላቸውን ፍቅርና ክብር ገለጹ (ቪድዮ ይዘናል)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ትናንት ሜይ 31 ቀን 2014 ዓ.ም በሚኒሶታ ከጃኪ ጎሲ ጋር በመሆን የሙዚቃ ኮንሰርቱን ያቀረበው ቴዎድሮስ ታደሰ በተመልካቹ ከፍተኛ አድናቆትን አገኘ። በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ስሙ ከፍ ብሎ የሚነሳው ቴዎድሮስ ታደሰ በሚኒሶታ ባቀረበው የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ ተወዳጅ ዘፈኖቹን ያቀረበ ሲሆን በየዘፈኑ መካከል ሕዝቡ ለድምጻዊው ያለውን ፍቅር እጁን በማውለብለብ፣ በፉጨት፣ በጭብጨባ፣ በመጮህ የገለጸ ሲሆን አንድ ዘፈን ዘፍኖ በጨፈረ ቁጥር ደግሞ ሕዝቡ “ቴዲ… ቴዲ… ቴዲ..” እያለ ስሙን በመጥራት ድምጻዊውን አክብሮት አምሽቷል።
tewedros tadesse
ድምፃዊ ቴዎድሮስ ታደሰ በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ከተሞች እየተዘዋወረ እያቀረበ ያለው የሙዚቃ ኮንሰርት የሚቀጥል ሲሆን በመድረክ እያሳየ ያለው ድንቅ ብቃት ሕዝቡን አስደምሟል። ዘ-ሐበሻ በሙዚቃ ኮንሰርቱ ውስጥ ከነበሩ ታዳሚዎች አስተያየት መረዳት እንደቻለችው ሕዝቡ ለቴዎድሮስ ታደሰ ከፍተኛ ክብርና ፍቅር እንዳለው ነው።

የሙዚቃ ሕይወቱ ከቤተክርስቲያን የሚጀምረው ቴዎድሮስ ታደሰ በቅርቡ አንድ ሲዲ ያወጣ ሲሆን በትናንትናው የሚኒሶታ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ ይህ ሲዲ ሲሸጥ እንደነበር ለማየት ችለናል፡፡

ትናንት በሚኒሶታ ቴዎድሮስ ታደሰ ካቀረባቸው ዘፈኖች መካከል ዘ-ሐበሻ ለአንባቢዎቿ አንዱን ቪድዮ እንደሚከተለው አካፍላለች።

ፍርድ ቤቱ ባለፈው ውድቅ ያደረገውን ጉዳይ ዛሬ ያለምንም ይግባኝ ማፅደቁ ተሰማ

$
0
0
10357ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2006 ዓ.ም. የነበረው የፍርድ ቤት ውሎ አዲስ ክስተትን ይዞ ብቅ ማለቱ ተሰምቷል፡፡ ባለፈው ሚያዚያ 2006 ዓ.ም.ተጠርጥረው ከታሰሩ 3 ጋዜጠኞች እና 6 ብሎገሮች መካከል ዛሬ እሁድ ግንቦት 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀጠሮ የነበራቸው በፍቃዱ ኃይሉ፣ አቤል ዋበላ እና ማህሌት ፋንታሁን ቀደም ሲል የማዕከላዊ ፖሊስ ጉዳዩን ወደ ፀረ-ሽብርተኝነት የክስ ጉዳይ ለመውሰድ የጠየቀው በፍርድ ቤቱ ውድቅ ተደርጎ የነበረ ቢሆንም፤ ዛሬ በሌላ ተቀያሪ ወንድ ዳኛ እዛው ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት ባለፈው በነበረው ቀጠሮ ውድቅ የተደረገው በፀረ-ሽብርተኝነት ክስ ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ 28 ቀናት የምርመራ ጊዜ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ በዛሬው ውሎ የነበፍቃዱ ፣ አቤል እና ማህሌት ሂደት ለሰኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡በጉዳዩ ላይ ጥያቄ ያቀረብንላቸው ተከላካይ ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንን፤ ከህግ አኳያ ፖሊስ ጉዳዩን ወደ ፀረ-ሽብርተኝነት ጠይቆ ውድቅ ተደርጎበታል፣ ስለዚህ በነበረው ውሳኔ ፖሊስ ቅር ከተሰኘ ይግባኝ ማለት እንጂ በተመሳሳይ ችሎት እና ጉዳይ ላይ በፍርድ ቤቱ ውድቅ የተደረገ ጉዳይ እንደገና ቀርቦ የፖሊስ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ እና ተጨማሪ የ28 ቀናት የምርመራ ጊዜ በሚል መፈቀዱ ከህግ አግባብ ውጭ ነው፤ ይሄንንም ለፍርድ ቤቱ ብናቀርብም ተቀባይነት አላገኘም፤ ስለዚህ የህግ አካሄድ (procedure) ስህተት ታይቶበታል ሲሉ የነበረውን ሂደት ተናግረዋል፡፡ ይህን የክስ ሂደት ፖሊስ ጉዳዩን ወደ ፀረ-ሽብርተኝነት ለመውሰድ ውድቅ ያደረገችው ዳኛ ሴት እንደነበረች አይዘነጋም፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የነገረ-ኢትዮጵያ ጋዜጠኛ በላይ ማናየ ፖሊስ ፍርድ ቤት ያቀረባቸውን እስረኞች ሲያወጣ፤ ለተወሰነ ጊዜ በጠበቂ የፀጥታ ኃይሎች ለጊዜው ታግቶ እንዲቆይ ከተደረገ በኋላ፤ ለነገ ማዕከላዊ እንዲቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ተለቋል፡፡ ለተወሰነ ጊዜ የተደረገው የጋዜጠኛው እገታ ምክንያት እስካሁን አልታወቀም፡፡

(Bisrat Woldemichael/Addis Ababa)

 — with Izedine Yahya.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>
<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596344.js" async> </script>