Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

“የኢትዮጵያ የብሔሮች ጥያቄና መፍትሔዉ” እስክንድር ነጋ(ከቃሊቲ እስር ቤት)

$
0
0

 

እስክንድር ነጋ

እስክንድር ነጋ

የዲሞክራሲያዊ መብቶች ጋር ተያይዞ፣ የብሔረሰቦች የእኩልነት መብት በቃልና በፕሮግራም ብቻ ሳይሆን፣ በግብር መታወቅ አለበት፡፡ የእያንዳንዱም ብሔረሰብ ቋንቋ፣ ባህል፣ ሃይማኖትና ሌሎችም መለያዎች በእኩልነት መታወቅና መከበር አለባቸዉ፡፡ ብሔሮች ሁሉ ትልቅም ሆነ ትንሽ የራሳቸዉን የወደፊት ዕድል የመወሰን መብት መታወቅና በትክክል ከስራ ላይ መዋል አለበት፡፡ ብሔሮች ቋንቋቸዉንና ጠቃሚ የሆኑትን ባህሎቻቸዉን በነፃ እንዲያዳብሩ መደረግ አለበት፡፡ ማንም ሰዉ በዉስጥ አስተዳደራቸዉ ላይ ጨቋኝ ተፅዕኖ እንዳያደርግ መከላከል አለበት፡፡ ኢትዮጵያን ከብሔሮች እስር ቤትነት ወደ ብሔሮች ማበቢያ ሥፍራ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ይቻላልም፡፡ የሕዝቦች አንድነት፣ በሳንጃና በመድፍ በተቋቋመዉ አንድነት ፋንታ፣ በመግባባትና በመፈቃቀድ ላይ ሊመሠረትና እንደአለት ጸንቶ ሊኖር የሚችለዉ በዚህ መንገድ ብቻ ነዉ፡፡ በንጉሱ እና በደርግ ጊዜ የብሔርን ጥያቄ አንግበዉ የተነሱ አካላት ሕዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ(ሻቢያ)፣ ሕወሓት እና ኦነግ ነበሩ፡፡ በአሁን ግዜ ግን ነፃ አዉጭ ብሔር የሌለዉ የደቡብ ክልል ብቻ ነዉ ይህም ሊሆን የቻለዉ እንደሚመስለኝ የጎሳዎች ብዛት እና የመልክአምድራዊ አቀማመጥ ብሎ ነግሮኛል፡፡ አምባገነን ባለበት አገር ላይ የብሔር ጥያቄ የሚያነሱ አካላት እየበዙ እንጅ እያነሱ አይሄዱም፡፡ እንደ ምሳሌ ታላቋን ሩስያ ማንሳት በቂ ነዉ፡፡ በእስታሊን አምባገነንነት ምክንያት አብዛኞቹ አገሮች ለመገንጠል ምክንያት ሆናቸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የዩጎዝላቪያ፣ የራሽያ እና የሶማሊያ እጣ ፋንታ ሳያጋጥማት እኛ ቀድመን ልናድናት ይገባል፡፡ ይሄም ሊሆን የሚችለዉ በአንድ እና አንድ መንገድ ብቻ ነዉ፡፡ እሱም በሰላማዊ ትግል ወያኔን ስናስወግድ ብቻ፡፡ከዛም ስራዉ የኛ የጋዜጠኞች እና የፖለቲከኞች ይሆናል፡፡ የብሔር ፖለቲካ የበሰበሰ እና ያለፈበት መሆኑን ምርጫ 1997 አስተምሮን አልፏል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ኤርትራ እንዳትገነጠል የበኩልን ድርሻ ቢወጣም በወያኔ እንቢተኝነት በ1984 ዓ.ም ምህረት ህዝቡን አሰሩ፣ ገደሉ አቆሰሉ፡፡ ይህም አልበቃ ብሏቸዉ የኤርትራ ህዝብን በምርጫ በማወናበድ ምርጫቸዉን አሳኩ፡፡ በየት አገር ነዉ ባርነት ወይስ ነፃነት የሚል ምርጫ የተካሄደባት አገር አለች፡፡የኤርትራ ህዝብ ግን የጣሊያን እና የእንግሊዝ አስተዳደር አሻፈረኝ ብሎ ወደ እናት አገራቸዉ ለመመለስ የበኩላቸዉን ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናቶች ይናገራሉ፡፡ ሁለት ኤርትራዊያን ግለሰቦችን ማንሳት ያዉም በቂ ነዉ ዘርዐይ ደረስ ጣሊያኖች በኢትዮጵያ ባንዲራ ላይ ሲቀልዱ በመበሳጨት ጣሊያኖች ላይ ጉዳት አድርሷል፤ አብርሃም ደቦጭ በግራዚያኒ ላይ ቦምብ በመወርወር የመግደል ሙከራ ያደረገ እና ያቆሰለ፡፡ህዝቡም ሲጠይቅ የነበረዉ ኢትዮጵያዊነት ነዉ፡፡ይህንንም አሳክተዉ ከ60 ዓመታት በኋላ ተመልሰዋል፡፡ ለዚህ ሁሉ መሳካትም የዉጭ ጉዳይ ሚኒስተር የነበሩት የአክሊሉ ሀብተወልድ ድርሻ ላቅ ያለ ነበር፡፡


“ኢትዮጵያ ወይም ሞት” በማለት በሀገር ፍቅር ማህበር ስር የተሰለፉ ሀገር ወዳድ ኋይሎች ህዝቡን በማስተባበር በነቂስ ወጥቶ የኤርትራን ግዛቶች ሲያጥለቀልቅ እንደነበርም ይታወሳል፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር አብረዉ ለመኖር የሚፈልጉ ህዝቦች ነበሩ፡፡ ሁሉም የኤርትራ ህዝብ ለመገንጠል ከሻቢያና ከወያኔ ጋር አብረዉ ቁመዋል ማለት ከእዉነት የራቀ ነዉ፡፡ የኤርትራ መገንጠል ለአስገንጣኞች አካላት ብቻ ነዉ የጠቀመዉ፡፡ ኤርትራ በመገንጠሏ የኤርትራ ህዝብ ምን አገኘ? የኢትዮጵያ ህዝብስ ምን አገኘ? አሁንም የኤርትራ ህዝብ በጭቆና፣ በርሀብ፣ በስደት እና በበሽታ እያለቀ ነዉ፡፡ መገንጠል እንደማያዋጣ የኛዉ ኤርትራ አስተምራናለች፡፡
እስክንድር ነጋ የሚፈልገዉ እኩልነትና ነፃነት የሠፈነበት፣ የህዝቦቿ አንድነት ከብረት የጠነከረባትና ብሔረሰቦች ሁሉ ያበቡባት፣ የማንም ተመፅዋች ያልሆነ በራሱ የሚተማመን በማንም ፊት የባታችነት ስሜት ሊኖረዉ የሚችል ህዝብ እንዲይፈጠር ነዉ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ትግል የፈጀዉን ጊዜ ቢፈጅምና የፈለገዉን ያህል መሥዋዕትነት ቢጠይቅም፣ ብዙ ችግሮችና መሰናክሎችን ከፊታችን ቢደቀኑም፤ የዚች ዓይነት ኢትዮጵያ እንድትመሰረት እስከ መጨረሻዉ ለመታገል ቆርጨ ተነስቻለዉ፡፡ የእናት አገራችን ህልዉና ላያስጠብቅ የሚችለዉ ለ22 ዓመታት ፈላጭ ቆራጭ ጫማ ስር የተረገጠችበት ብሔራዊ ነፃነቿን ክብሯ ተገፍፎ የቆየችበት ዓመታት ነዉ፡፡ በሁሉም ወገን የሚደረገዉ መሯሯጥና መሰናዶ ሲታይ አበረታታች ነዉ፡፡ ወሳኝ የሆነዉ ፍልሚያ ገና ከፊታችን እንደሚጠብቀን ምንም ጥርጥር ሊኖረዉ አይችልም፡፡
የግንቦት 7 መስራች እና መሪ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በሚመለከት ከግብፅ መንግስት እርዳታ ተቀብሏል ተብሎ ወሬ እየተናፈሰ መሆን ስጠይቀዉ፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ብርሃኑ የሚያደርገዉ አይመስለኝም ካደረገዉ ግን በጣም አዝኘበታለዉ፡፡ ለምንድን ነዉ አባቶቻችን የሰሩትን ስህተት የምንደግመዉ፡፡ መኢሶን፣ ኢህአፓ፣ ጀብዐ እና ወያኔ በአንድ ይሁን በሌላ መልኩ የዉጭ እርዳታን እየተቀበለዉ፡፡ አገራችን እና ህዝቧን ጎርቷል፡፡ ኤርትራን እንድናጣ ሁነናል፡፡ አሁንም መናገር የምፈልገዉ ኢህአዴግን እና ኢትዮጵያን ለይተን ማዬት አለብን፡፡ ኢህአዴግን የጎዱ እየመሰላቸዉ አገራችንን እያደሟት ነዉ፡፡
ለተቃወሚ ፓርቲዎች እችን መልዕክት አስተላልፏል፡፡
1.የዉጭ ኋይሎች ድጋፍ የዚችን ኩሩና ታሪካዊ አገራችንን ብሔራዊ ክብርና ነፃነት የማይነካ፣ ራስን ለመቻል የምታደርገዉን ጥረት የሚያግዝ እንጅ የማያደናቅፍ እርዳታ መሆን አለበት፡፡
2. ማንኛዉም ህዝብ በዉጭ እርዳታ ላይ በመተማመን አብዮቱን ከግብ ለማደረስ እችላለሁ ብሎ ካሰበ ራሱን ማታለሉ ብቻ ሳይሆን አብዮቱንም ብሔራዊ ነፃነቱን ያጣል፡፡ ማንም ህዝብ በተለይም ደግሞ እንደኢትዮጵያ ሕዝቡ ኩሩና ባለታሪክ ሕዝብ ከሆነ ለገዛ ነፃነቱ፣ ለገዛ ለዉጡ ለገዛ ክብሩ ከሁሉም በፊት መተማመን ያለበት በራሱ መሆኑ መታወቅ አለበት፡፡ ስለሆነም የዉጭ እርዳታን በሚመለከት በኩል ብሔራዊ ክብርና ነፃነት እንደዚሁም ከሁሉ በፊት በራስ መተማመን የሚለዉ ዋናዉ መመሪያችን ይሆኑ፡፡
እስክንድር ነጋ
ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫ ጊዜያቸዉን ማባከን የለባቸዉም የሰማያዊ ፓርቲ እና አንድነት ፓርቲ የሰላማዊ ትግል መንገድ መቀላቀል አለባቸዉ፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲ “ሰላማዊ ትግሉን(አብዮቱን) እኛ ካልመራነዉ አብዮት አይሆንም” ከሚል አመለካከት መጀመሪያ መላቀቅ አለባቸዉ፡፡ትግሉን ማንም ይምራዉ ማን ሕዝቡ ለትክክለኛዉ የስልጣን ባለቤት መሆን አለበት፡፡ ዛሬ የሚወነጃጀሉት ኢህአፓ፣ መኢሶን፣ ማሌሪድ፣ ሰደድ፣ ወዝ ሊግ፣ ሻዕቢያ፣ ህወሓት ይህን የህዝብ መብት ረግጠዉ እና አፍነዉ በህዝቡ ቦታና ጥያቄ እራሳቸዉን መተካታቸዉ ሲሆን ዋና የህዝቡን የበመደል መነሻ ምክንያት ይህ ነዉ፡፡ በመሆኑም በአንዳንድ ታዳጊ አገሮች ዉስጥ ሕዝቡን በዙሪያቸዉ አጠቃለዉ ለማሰለፍ አይነት ተግባራዊነት ታላላቅ ሰዎችን የመሰሉ እንኳን ለማፍራት አልቻለችም፡፡ ከዚህ አኳያ ጋንዲን ያፈራች ህንድ፣ ማኦን ያፈራች ቻይና፣ ማንዴላን ያፈራች ደቡብ አፍሪካ እና ፓትርስ ሉሙባን ያፈራች ኮንጎ ጋር ሀገራችን በአቻ አትታይም፡፡ እነዚህ ታላላቅ ሰዎች ከሀገራቸዉ አልፈዉ የአለም ሰዎች ሁነዉ ኑረዋል፡፡እየኖሩም ነዉ፡፡ እንዲያዉም ኢትዮጵያ ዛሬ የጎደላት ነገር ቢኖር እኒህን የመሰሉ ቅን ሰዎችን ማግኘት ነዉ፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ እንኳን የብሔረሰቦችን የአመለካከት ድንበር አቋርጦ በማለፍ የህዝቦቷን አመኔታ ሊያገኝ የቻለ የፖለቲካ ሰዉ መፍጠር ቀርቶ ለተወለደበት ብሔረሰብ ለመቆም የቻለ ሀቀኛ የህዝብ ሰዉ መፍጠር አልተቻለም፡፡
በመጨረሻም እስክንድር ልብን በሚማርክ ሁኔታ ስለ ኢትዮጵያ እናት እና አባቶቻችን ለብዙ ዓመታት ታግለዉና ተዋግተዉ ነፃነታቸዉን ያወጁት፡፡ ስለዚህ ይህ ትዉልድ ጭቆናና ግፍ በቃኝ ብሎ የራሱን መሪዎች ገርስሶ መጣል አለበት፡፡
“እኔ ለዲሞክራሲ ስል ታሰርኩ እንጅ ሌላ ምን ሆንኩኝ ለነፃነት የምከፍለዉ መስዋዕትነት እስከ ሞት ድረስ ነዉ”
እስክንድር ነጋ
“እኔ ከኢትዮጵያ የተሻለ አገር የለኝም የምታሰርባት፣ የምገረፍላት፣ የማለቅስላት፣………. በቃ በአጭሩ እኔ የምሞተዉ በአገሬ በኢትዮጵያ መሬት ነዉ፡፡ ነፍሴም የምታልፈዉ ሥጋዬም የሚፈርሰዉ በምወዳት አገሬ ኢትዮጵያ ነዉ”
እስክንድር ነጋ
“ብሔሮች በጋራና በሰላም ለመኖር ዘላለማዊ ዋስትናቸዉ ደግሞ ዲሞክራሲያ መንግስት ነዉ”
እስክንድር ነጋ
ጠያቂዎቹ እየበረከቱ ሲመጣ ቻዉ ተባብለን ተለያየን በሌላ ቀን እነዚህን አይጠገቤ ወሬዎችህን እንደምትደግምልኝ ተስፋ አረጋለዉ፡፡
አምላክ ከአንተ ጋር ይሁን ብዬ ወጣዉ፡፡
ከእስክንድር ዐይን ርቄ በሄድኩኝ ቁጥር ሆድ ባሰኝ አቅም አነሰኝ ይህን ንፁህ ሰዉ ማሰር ምን ይሉታል፡፡
በረከት ስምዖን፣ አባይ ፀሐዬ፣ ሳሞራ የኑስ…………… ተዉ ፍቱ ይህን ጀግና፡፡
ተዉ ተዉ ተዉ………… ከሆስኑ ሙባረክ፣ ከጋዳፊ ተማሩ፡፡
ቅዳሜ ጧት 3፡00-3፡30(ከቃሊቲ እስር ቤት)
አብዲሳ አጋ(ገሞራዉ)


በድር ድርጅታችን ወደ የት እያመራ ነው? (ፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን)

$
0
0

ነገ አርብ ሜይ 9 በሚኒሶታ በሚደረገው ሰልፍ ኢትዮጵያውያን ተገኝተው ድምጻቸውን በጋራ እንዲያሰሙ ጥሪ ቀረበ

$
0
0

st paul Minnesota selef
(ዘ-ሐበሻ) በሃገራዊ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን የሚያደርገው የሚኒሶታ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ማህበር ነገ በሚኒሶታ የኦሮሞ ኮምዩኒቲ በጠራው ሰልፍ ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያውያን ወዳጅ የሆነ በመገኘት አንባገነኑ የሕወሓት መንግስት ሰላማዊ ጥያቄ ባቀረቡ ዜጎች ላይ በተለያዩ የኦሮሚያ ክልሎች የወሰደውን የግድያ እርምጃ እንዲያወግዝ ጥሪ አቀረበ።

“አስቸኳይ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ! በሚኒሶታ ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያውያን ወዳጆች” በሚል የወጣቶች ማህበሩ በሶሻል ሚድያ፣ በቴክስት መልዕክት፣ በፖስተርና በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች እየበተነ ካለው በራሪ ወረቀት ላይ እንደሚነበበው “አምባገነኑ የሕወሓት/ኢሕአዴግ መንግስት ከዚህ ቀደም በአፋር፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በትግራይ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በኦጋዴንና በሌሎችም የኢትዮጵያ ከተሞች ሰላማዊ ጥያቄ ባነሱ ዜጎች ላይ ይወስድ የነበረውን በጥይት የመግደል ዘመቻ በመቀጠል ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል ሰላማዊ ጥያቄ ያነሱ ተማሪዎችን ጥይት በመተኮስ መግደሉ ይታወሳል። በመሆኑም በሚኒሶታ የሚገኘው የኦሮሞ ኮምዩኒቲ ከሜይ 9 ቀን 2014 (May 9, 2014) ጀምሮ በሴንት ፖል ስቴት ካፒቶል ደጃፍ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ከጠዋቱ 9 ሰዓት ጀምሮ የጠራ በመሆኑ፤ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ጥቃት በጋራ እናወግዝ ዘንድ ሁላችሁም ተጠርታችኋል። ዝምታ በቃ! ጥይት በቃ!” ይላል።

በነገው ዕለት ሜይ 9 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 9 ሰዓት ጀምሮ በሚኒሶታ ስቴት ካፒቶል (Minnesota State Capitol፡ 75 Rev Dr Martin Luther King Jr Boulevard., St Paul, MN 55155) የሚጀመረው የተቃውሞ ሰልፍ ቀጣይነት እንደሚኖረው የተገለጸ ሲሆን ሕዝቡ በነቂስ በመውጣት ድርጊቱን እንዲያወግዝ ማህበሩ ጥሪውን አቅርቧል።

ማህበሩ ከነገው ተቃውሞ በተጨማሪ “በቅርቡ የወያኔ ሰዎች በሚኒሶታ እናደርገዋለን ያሉትንና በአላሙዲ የሚደገፈው የስፖርት ፌስቲቫል ቦይኮት ለማድረግ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረጉ እንደሚገኙ” ገልጸው “ወያኔዎች ኢትዮጵያ ሰው እየገደሉ ሚኒሶታ መጥተው በደም ገንዘብ ጨፍረውብን አይሄዱም” በሚል መርህ እቅዳቸውን ለማክሸፍ እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ በበተኑት ወረቀት ላይ ገልጸዋል።

ግንቦት 7 በተማሪዎች እንቅስቃሴ ዙሪያ፡ “በወያኔ ዘረኛ ፕሮፖጋንዳ ተጠልፈው ሕዝብን ከሕዝብ ጋር የሚያቃቅሩ ሰዎችን አትስማ”

$
0
0

ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ በግፍ ሕይወታቸው ባጡ ዜጎች መርዶ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እና ቁጭት ይገልፃል፤ ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናትን ይመኛል። ህወሓት እና አጋፋሪው ኦህዴድ በነዙት ሽብር ሳቢያ የአካል ጉዳት የደረሰባችሁ፣ የተደበደባችሁ እና ለእስር የተዳረጋችሁ ወገኖቻችንም ህመማችሁም እስራችሁም የሁላችንም ነው። መላው ኢትዮጵያዊ ወገናችሁ ከእናንተ ጋር ተገድሏል፣ ቆስሏል፣ ተደብድቧል፣ ተግዟል፣ ታስሯል። ህወሓት፣ ኦህዴድ እና በዚህ ጭፍጨፋ እጃቸው ያለበት ሁሉ ከተጠያቂነት የማያመልጡ መሆኑን ግንቦት 7 ደጋግሞ ያስገነዝባል።
ginbot 7
በህወሓት ዘረኛና ፋሽስታዊ አገዛዝ ያልተበደለ የኢትዮጵያ ክፍል የለም። የወያኔ አጋፋሪ የሆነው አህዴድ የኦሮሞ ወጣቶችን፣ ሕፃናትንና አዛውንትን ሲጨፈጭፍና ሲያስጨፈጭፍ፣ ሌላው አጋፋሪ ብአዴን ደግሞ በጎንደርና አካባቢው ተመሳሳይ ጭፍጨፋዎችን አካሂዷል። ወያኔ ከፋሺስት ኢጣልያ ወርሶ ለሃያ ዓመታት በትጋት ያራመደው “የከፋፍለህ ግዛ” ፓሊሲ ምርት እነሆ ዛሬ በዓይኖቻችን እያየን ነው። ፋሽስት ጣልያን ጀምሮት የነበረውን ኢትዮጵያን የማጥፋት ስትራቴጄ ለማጠናቀቅ ህወሓት በጥድፊያ ላይ ነው። ይህን እኩይ ዓላማ ማስቆም የሁላችን ኃላፊነት ነው።

የመከላከያ ሠራዊት እና የፊደራል ፓሊስና አባላት ሆይ፣ ለዘረኛው ወያኔ መሣሪያ ሆናችሁ ወገናችሁን አትፍጁ! እናንተ የምታገለግሉት ሥርዓት፣ ከእናንተ መካከል ኦሮሞ ያልሆኑት እየመረጠ ኦሮሞዎች ወገኖቻችንን እንዲገሉ፣ አማራ ያልሆኑት ተመርጠው አማሮችን እንዲገሉ የሚልክ መሠሪ መሆኑን የምታውቁት ነው። ወኔን አንዳችንን በሌላችችን ላይ እያዘመተ እርስ በርስ ሊያፋጀን ቆርጦ መነሳቱን አስተውሉ። ይህን እኩይ ዓላማ የማክሸፍ ሥራ የናንተም ኃላፊነት እንደሆነ ግንቦት 7 ያስገነዝባል።

በወያኔ የስለላ መዋቅር ውስጥ ያላችሁ ህሊና ያላችሁ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን የምትሠሩት ሥራ አገራችን ወደየት ሊወስዳት እንደሚችል ቆም ብላችሁ አስተውሉ። እናንተ ዛሬ የምትወስዱት ቆራጥ እርምጃ የበርካታ ሕዝብ ሕይወት ሊታደርግ ይችላል።

የኢትዮጵያ ወጣቶች በተለይም የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ተከፋፍላችሁው ወያኔን መቃወም የትም አያደርስም። በኦሮሞው መገደል አማራው፣ ትግሬው፣ ወላይታው፣ ጉራጌው ካላመመው፤ አማራው ሲበደል ኦሮሞውና ሌላው እንዲያመው እንዴት መጠበቅ ይቻላል። እናንት ወጣቶች ከዘውግ ቆጠራ በላይ ሁኑ። ዛሬ የሚደረጉ ትናንሽ ነገሮች እንኳን የረዥም የወደፊት ውጤት እንዳላቸው ተገንዘቡ። የወደፊቱ ኢትዮጵያ የእናንተ ናት፤ የምትመኟችን ከራሷ ጋር የታረቀች ኢትዮጵያን ለመፍጠር በቅድሚያ እናንተ መታረቅ ይኖርባችኋል። የሁላችንም ቀንደኛ ጠላት ወያኔ ነው ትኩረታችሁን እሱ ላይ አድርጉ።

ውድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!!!! አውቀውም ሆነ ሳያውቁ በወያኔ ዘረኛ ፕሮፖጋንዳ ተጠልፈው ንግግራቸው ሰው ሕዝብን ከሕዝብ ጋር የሚያቃቅሩ ሰዎችን አትስማ። የመረረ፣ የሚያስቆጣ ንግግር እንኳን ቢናገሩ ንቀህ ተዋቸው። በወያኔ ውስጥም ሆነ ከወያኔ ውጭ ሆነው ብሔርና ዘርን እያነሱ ተማረው ማስመረር የሚሹ ሁሉ ግባቸው አንድ ነው። በየትናቸው ወገን ቢሆኑ እነሱ የጥፋት ኃይሎች ናቸው፤ እነሱ የኢትዮጵያና የሕዝቧ ጠላት የሆነው የህወሓት መጠቀሚያ ናቸው።

በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት ህወሓት እና ህወሓት የዘረጋው ሥርዓት ነው። የጋራ ትኩረታችን በጋራ ጠላታችን ላይ ብቻ ይሁን። ወያኔ ትኩረታችን ለመበተን ብዙ ነገሮችን ይጀምር ይሆናል፤ ርስ በራሳችን ከማባላትም አልፎ ጎረቤቶቻችንን መጎነታተል ይጀምር ይሆናል። በእንዲህ ዓይነት ድርጊት ትኩረታችን መበተን ፈጽሞ የለበት።

እኛ ኅብረታችንን ስናጠናክር የተዳከመው ወያኔ ይበልጥ ይዳከማል። ሊበታትኑን የዳከሩትን አሳፍረን ኅብረታችን እናጠነክራለን። ይህ ደግሞ የወያኔ ውድቀት እና የኢትዮጵያ ትንሣኤን ያፋጥናል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

አበበ ገላው ዳግም ታሪክ ሰራ፤ በመለስ ላይ ያደረገውን በባራክ ኦባማ ላይ ደገመው (ቪዲዮ)

በግንቦት ወር የተከሰቱ 11 ታሪካዊ ሁነቶች

$
0
0

Meles zenawi

ከአቤኔዘር ይስሃቅ

1. ግንቦት 1, 1947 ዓ.ም ሀገራቸውን ከድተው ለጣሊያን በባንዳነት ሲያገለግሉ የነበሩት የአስረስ ተሰማ የልጅ ልጅ የነበረው የቀድሞው አምባ-ገነኑ፣ ከፋፋዩና ጎጠኛው መሪ ለገሰ/መለስ/ ዜናዊ የተወለደበት ቀን።

2. ግንቦት 8, 1981 ዓ.ም የሀገሪቱ ጄኔራሎች በመንግስቱ ሀይለማሪያም ላይ የመፍንቅለ መንግስት ሙከራ ያደረጉበት ቀን።

3. ግንቦት 8, 1982 ዓ.ም በመንግስቱ ኃይለማሪያም ላይ መፈንቅለ መንግስት ሙከራ ያደረጉት ጄኔራሎች የተረሽኑበት ቀን።

4. ግንቦት 13, 1983 ዓ.ም አምባ-ገነኑ፣ ሰው በላውና ጨፍጫፊው መንግስቱ ኃይለማሪያም ሀገሪቱን ጥሎ ወደ ዚምባቡዌ የፈረጠጠበት ቀን።

5. ግንቦት 16, 1983 ዓ.ም ሻዕቢያ የኢትዮዽያ ሁለተኛ ትልቅ ከተማ የነበረችውን አሥመራን የተቆጣጠረበት ቀን።

6. ግንቦት 20, 1983 ዓ.ም አምባ-ገነኑ ኢህአዴግ የቀድሞውን አምባ-ገነን ደርግን የተካበት ቀን።

7. ግንቦት 4, 1990 ዓ.ም ሻዕቢያ ኢትዮጵያን የወረረበት ቀን።

8. ግንቦት 7, 1997 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በነቂስ ወጥቶ በምርጫ የራሱን መሪዎች የመረጠበት ቀን። /በኋላ ኢህአዴግ ቢያጭበርብረንም/

9. ግንቦት 7, 1997 ዓ.ም ማታ ላይ መለስ የራሱን ሕገ-መንግስት ጥሶ ከግንቦት 8, 1997 ዓ.ም ጀምሮ ምንም አይነት ከቤት ውጪ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ መከልከሉን ያወጀበት ቀን። ከ8 አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ከመለስ ሞት በኋላ በመለስ የታወጀው ሕገ-ወጥ ክልከላ እንዲሻር ማድረጉ ይታወቃል።

10. ግንቦት 8, 1997 ዓ.ም በሀገሪቱ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ የምርጫ ቆጠራው ሳይጠናቀቅና ምርጫ ቦርድም ምንም አይነት መግለጫ ከመስጠቱ በፊት ኢህአዴግ ከአዲስ አበባ በቀር በሁሉም የሀገሪቱ ክልል ምርጫውን ማሸነፉን በጉልበት ያወጀበት ቀን።

11. ግንቦት 10, 2004 ዓ.ም አበበ ገላው በአሜሪካ የመለስን ቀልብ የገፈፈበትና መለስም በአደባባይ ሲደነግጥ የታየበት ቀን። ከድንጋጤው ሳያገግም ከዚያ በፊት የነበረበት ህመም ተባብሶበት ከ2 ወር በኋላ በዚያው ሞተ። የተረሳ ካለ ጨምሩበት።

Sport: ከኦልድ ትራፎርድ የሚሰናበቱ ተጨዋቾች (ግምታዊ የባለሙያ ትንታኔ)

$
0
0

ማንችስተር ዩናይትድ በአውሮፓም እጅ ሰጥቷል፡፡ በባየርን ሙኒክ ሲሰናበት ግን ሽንፈቱ የክብር እንጂ የውርደት አልነበረም፡፡ የዘንድሮውን የቡድናቸው ሁኔታ ጠንቅቀው የሚያውቁት የክለቡ ደጋፊዎችም አስቀድመው ከዚህ የላቀ ነገር አልተመኙም፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት እንግሊዝን ሊግ በአሳማኝ ብርታት ያሸነፈው ቡድን ዘንድሮ ብዙ ድክመቶችን እያሳየ ቆይቶ የውድድር ዘመኑን ሊያጠናቅቅ ተቃርቧል፡፡

man united
ዘንድሮ የሚፎካከርበት ምንም ዋንጫ ያልቀረለት ዩናይትድ አሁን ለከርሞው ለመዘጋጀት በቂ ዕድል ተፈጥሮለታል፡፡ የዝግጅቱ አንድ ስራ በክለቡ ሰፊ ለውጥ ማድረግ ነው፡፡ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን በርካታ አዳዲስ ተጨዋቾች በቀዩ ማሊያ ሊታዩ እንደሚችሉ ሁሉ ከክለቡ ጋር በርካታ ስኬቶች ያገኙ ነባር ከዋክብትም ይሰናበታሉ፡፡ በ2014/15 የውድድር ዘመን በኦልድ ትራፎርድ አይታዩም ተብለው የሚታሰቡትን ተጨዋቾች እንደሚከተለው መቃኘት ይቻላል፡፡

የጀግኖቹ ስንብት

የሪዮ ፈርዲናንድ፣ ኒማኒያ ቪዲች እና ፓትሪስ-ኤቭራ የኋላ ክፍል ጥምረት ማንችስተር ዩናይትድን በእንግሊዝ ብቻ ሳይሆን በአውሮፓ ለተከታታይ ዓመታት ውጤታማ አድርጓል፡፡ ቪዲች ክረምቱ ሲመጣ ኦልድ ትራፎርድን እንደሚለቅቅ አረጋግጧል፡፡ ኤቭራም የመሰናበቱ ነገር አይቀሬ ይመስላል፡፡ ፈርዲናንድ አካሉ እንደሚገባ አልታዘዝ ካለው ቆይቷል፡፡ ቀድሞ ከአውሮፓ ድንቅ ተከላካዮች አንዱ የነበረው ኮከብ አሁን ፈጽሞ ራሱን አይመስልም፡፡

እነዚህን ሶስት ተጨዋቾች መተካት ቀላል አይሆንም፡፡ ተከላካዮቹ እርስ በርስ ከነበራቸው ድንቅ ውህደት እና አስገራሚ የመከላከል ችሎታ በተጨማሪ በሜዳ እና ከሜዳ ውጪ ቡድናቸውን የመምራት አቅም ነበራቸው፡፡ በቀደሙት ዓመታት ዩናይትድ የኤድዊን ቫን ደር ሳርን አገልግሎት ከማጣቱ በፊት በጋራ የፈጠሩት እጅግ ጠንካራ የኋላ ክፍል አሁን በዕድሜ ተፅዕኖ ቦታውን የመልቀቂያ ጊዜ መጥቷል፡፡ ጊግስ የእነዚህን ተጨዋቾች ችሎታ የያዙ ፈራሚዎችን ብቻ ሳይሆን እነ ቪዲች ከቡድኑ የተከላካይ መስመር የሚያጎድሉትን የካበተ ልምድ የመተካት ከባድ ስራ ይጠብቃቸዋል፡፡

የመሀል አማካይ ክፍል

በማንችስተር ዩናይትድ ለዓመታት ተገቢውን ትኩረት ያላገኘው ክፍል ብለው የሚጠቅሱት አሉ፡፡በተለይ ከጃንዋሪ የሁዋን ማታ ከፍተኛ ዝውውር በፊት በክረምቱ ማርዋን ፌላይኒ ተገዝቶም የዩናይትድ የመሀከል ክፍል ደካማ ነበር፡፡ በእርግጥ የቤልጅየማዊው መምጣት የቡድኑን አማራጭ ጨመረ እንጂ የቡድኑን ጥራት ከፍ አላደረገውም፡፡ ማይክል ካሪክ የአምናውን ድንቅ ብቃቱን መልሶ ማግኘት አልቻለም፡፡ ሆኖም እንግሊዛዊው አሁንም ለቡድኑ በሚያበረክተው የሜዳ ላይ አስተዋፅኦ ከሌሎቹ አጣማሪዎቹ በእጅጉ የተሻለ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ካሪክ ለከርሞ ከቡድኑ ጋር አብረው እንደሚቆዩ ከሚታመንባቸው ተፈላጊ ተጨዋቾች አንዱ ነው፡፡

የዳረን ፍሌቸር እና ቶም ክሌቨርሊ ቆይታ አጠራጣሪ ቢሆንም ስኮትላንዳዊው ሙሉ ጤንነቱን መመለስ ከቻለ ማንቸስተር ዩናይትድን ለመርዳት በቂ ችሎታ እና ጠንካራ ልምድ አለው፡፡ በአንፃሩ ክሌቨርሊ ባለፉት ሁለት የውድድር ዘመናት የበዛ ትችት ያስተናገደ እና በደጋፊዎች ዘንድም ተቀባይነቱን ያጣ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ከእርሱ ድክመት የበለጠ ወጣቱ ዘንድሮ ለቡድኑ ውጤት ማጣት እንደ ሰበብ መነሳቱ እንደተጋነነ የሚያምኑ ትቂት አይደሉም፡፡ እንግሊዛዊው በኮሚዩኒቲ ሺልድ ዋንጫ ጨዋታ ማንቸስተር ሲቲን ሲገጥሙ ትኩረት ከሳበ በኋላ ብቃቱ ሊሻሻል አልቻለም፡፡ ሌላኛው ቡድኑን መልቀቁ አይቀሬ የሚመስለው ተጨዋች ጫማውን ይሰቅላል ተብሎ የሚጠበቀው ሪያን ጊግስ ነው፡፡ በብሪታኒያ የትውልዱ እጅግ ስኬታማ ኮከብ የሚሰኘው ዌልሳዊ ዘንድሮ እንዳበቃለት የሜዳ ላይ ደካማ ብቃቱ አሳብቆበታል፡፡ ከዚህ በኋላ በተጨዋችነት ሳይሆን ምናልባት ለወደፊቱ በዩናይትድ የአሰልጣኞች መቀመጫ የመታየት ዕድል እንደሚኖረው ግምቶችን አግኝቷል፡፡

የአጥቂ አማካዮች /የክንፍ ተጫዋቾች/

ማንችስተር ዩናይትድ በመሀል ሜዳ ያሉት የተጨዋቾች እጥረት በሌሎች ቦታዎች አይንፀባረቅም፡፡ ቡድኑ በተቀሩት ሚናዎች ጥሩ አማራጮች ነበሩት፡፡ ሳይጠበቅ አስደናቂ የውድድር ዘመን ያሳለፈው አድናን ያኑዛይ በምርጥ ብቃቱ ራሱን እና ቡድኑን ብቻ ሳይሆን ጫና ውስጥ የቆዩትን ሞዬስም ጠቅሟል፡፡ እንዲያውም በውድድር ዘመኑ የመጀመሪያ ወራት ወጣቱ የቡድኑ እውነተኛ አደጋ ፈጣሪ እና ብቸኛ በጎ ነገር መስሎ ነበር፡፡

የሁዋን ማታ ዝውውር ድንቅ ግዢ ነበር፡፡ በውድድር ዘመኑ አጋማሽ ማንቸስተር ዩናይትድ ከተቀናቃኙ ቼልሲ ያመጣው ስፔናዊ በቶሎ ውጤታማ ብቃት ለማሳየት የተቸገረ ቢመስልም ቀስ በቀስ ከቡድኑ ጋር መዋሃዱን በተግባር ማሳየት ጀምሯል፡፡ ዌይን ሩኒም በ10 ቁጥር ሚና ማጫወት የሚችለው ቡድ በዚህ ቦታ ብዙ አማራጮች አሉት፡፡ በኦልድ ትራፎርድ የአቅሙን እንዲጫወት እድሉ ያልተሰጠው እና በማይመቸው ቦታ እንዲጫወት እየተደረገ የቆየው ሺንጂ ካጋዋ ሌላኛው የቦታው ድንቅ አማራጭ ነው፡፡ ዩናይትድ ምናልባት በሁኔታዎች ተገድዶ ባለተሰጥኦውን ጃፓናዊ በክረምቱ ሊለቀው እንደሚችል መገመት ይችላል፡፡ ይሁን እንጂ ከሩኒ እና ሮቢን ቫን ፔርሲ ጉዳት በኋላ እስያዊው ከማታ ጋር ያሳየው ድንቅ መግባባት ምናልባት ለመቆየቱ ሰበብ ሊሆን ይችላል፡፡

የክንፍ ተጨዋቾቹ ጉዳይ ግራ አጋቢ ነው፡፡ በማንቸስተር ዩናይትድ በቁጥር ጥቂት የማይባሉ የመስመር ተጨዋቾች ቢኖሩም ባለፉት ሁለት ዓመታት ውጤታማ መሆን ከብዷቸዋል፡፡ በተፈጥሯዊው የክንፍ ሚና ድንቅ ችሎታ ያላቸው አንቶኒዮ ቫሌንሲያ፣ ሉዊስ ናኒ እና አሽሊ ያንግ የሚችሉትን እንኳን ለመስራት የተቸገሩበት እንዲሁም በተመሳሳይ መልኩ የሶስቱም ብቃት ለረጅም ጊዜ ወርዶ የመቅረቱ ሰበብ ብዙ ግልፅ አይደለም፡፡ በተለይ ያንግ ወደ ክለቡ ከመጣ ጀምሮ ይህን ነው የሚባል ያልዋዠቀ ብቃት ማሳየት አልቻለም፡፡ የዩናይትድ ደጋፊዎች ከልባቸው ስንብታቸውን በጉጉት ከሚጠብቁባቸው ተጨዋቾች ቀዳሚው ያንግ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ካስቆጠራቸው ጎሎች እና ለጎል ካቀበላቸው ኳሶች ይልቅ ስሙ በይበልጥ ሳይነካ አስመስሎ ከመውደቅ ጋር በተደጋጋሚ መነሳቱም ለክለቡ አፍቃሪዎች ጥሩ ስሜት አልፈጠረም፡፡

ናኒ እና ቫሌንሲያ ቀደም ባሉት ዓመታት ከያንግ በተሻለ ቡድናቸውን ቢጠቅሙም የሚገባቸውን አገልግሎት ሰጥተዋል የሚባሉ አይደሉም፡፡ የፖርቹጋላዊው የኦልድ ትራፎርድ ህይወት ብዙ ተስፋ ተደርጎበት ኖሮ አሁን ወደ ተስፋ አስቆራጭነቱ ቀርቧል፡፡ በክረምቱ ናኒ ከተሰናባቾቹ መካከል ቢገኝ የሚያስደንቅ አይሆንም፡፡ እንደ ናኒ ሁሉ ክርስቲያኖ ሮናልዶን ሊተካ ይችላል ተብሎ መጠነኛ ግምት አግኝቶ በሰር አሌክስ ፈርጉሰን ብዙ ዕድል የተሰጠው ኢኳዶራዊው ከተፈጥሯዊ የክንፍ ሚናው ይልቅ ፉልባክ ሆኖ መጫወት ወይም ይበልጥ አፈግፍጎ የመስመር ተከላካይን የሚያግዝ አይነት ተጨዋች ሆኗል፡፡

አጥቂዎች
Danny-Welbeck-2011-manchester-united-218x300
ጊግስ የተጫዋች እጥረት ሳይኖርበት ብዙ የተቸገረበት የቡድኑ ክፍል ነው፡፡ ሩኒ እና ቫን ፔርሲ በግላቸው ድንቅ አጥቂዎች ቢሆኑም እርስ በርስ ሲጣመሩ ግን ውጤታማነት ሳይጎላቸው ለቡድኑ የመጨረሻ አቅማቸውን እንዳይጠቀሙ የሚያግዳቸው እንከን አላጡም፡፡ የሁለቱ በጋራ መጫወት በከፍተኛ የዝውውር ሂሳብ የተገዛውን ማታ ወደ ክንፍ ይገፋል፡፡ ብሎም ቡድኑ ከስፔናዊው ሊያገኝ የሚችለውን ጥቅም እያጣ ነው፡፡ ምናልባት ዩናይትድ እጅግ ፈታኙን እና ከባዱን ውሳኔ የሚያስተላልፍ ከሆነ እርምጃው የሚጀምረው በዚህ ቦታ እንደሚሆን መናገር ይቻላል፡፡ ኮንትራቱን በቅርቡ ካራዘመው እና በቀጣይ ክለቡን ለዓመታት የማገልገል አቅም ከያዘው ሩኒ ይልቅ ቫን ፔርሲ በክረምቱ ድንገት ሊሰናበት ይችላል፡፡

ዳኒ ዌልቤክ እና ሀቪዬር ሄርናንዴዝ የቋሚ ተሰላፊነትን ዕድል ለማግኘት ብዙ ቢመኝም እስካሁን ብዙ ጨዋታዎችን እያደረጉ ያሉት ከተጠባባቂ ወንበር በመነሳት ነው፡፡ ዌልቤክ እንደ አስፈላጊነቱ ከክንፍ እየተነሳ ማጥቃት ቢችልም ቺቻሪቶ እንደ ጎል ጨራሽነቱ ከፊት መስመር ሌላ ሚና መውሰድ አይችልም፡፡ ማክሲኳዊው በኦልድ ትራፎድ በዋና ቡድኑ ድንቅ ብቃት ማሳየት የጀመረው የዛሬ ሶስት ዓመታት ቢሆንም እስካሁን ቋሚ ተሰላፊ አይደለም፡፡ እንዲያውም በሞዬስ ስር የሚሳተፍባቸው ጨዋታዎች ብዛት ቀንሶበት ነበር፡፡

ሄርናንዴዝ የትኛውም ክለብ በቡድኑ ሊኖረው የሚመኘው አይነት ተጨዋች ነው፡፡ ከሜዳ ላይ ብቃቱ ሌላ ሁልጊዜም ፊቱ ላይ ፈገግታ አለመታጣቱ ጥሩ የመልበሻ ክፍል ሰው ያደርገዋል፡፡ ይሁን እንጂ አሁን በወሳኝ ዕድሜው ላይ የሚገኘው አጥቂ የተሻለ የመጫወት ዕድል ለማግኘት ወደ ውጪ ቢመለከት አያስደንቅም፡፡

Health: ሸንቀጥ ማለት ትፈልጊያለሽ?

$
0
0

hayat
የተስተካከለ የሰውነት አቋም ለመያዝ እና ሸንቀጥ ባለ ቁመና ለመታየት ከአመጋገብ በተጨማሪ የሰውነት እንቅስቃሴን ማድረግ ጠቃሚ እንደሆነ አሌ የሚባል ሀቅ አይደለም፡፡ ይህንን ስንል ለየትኛው ሰውነት ክፍል ምን አይነት እንቅስቃሴ ማድረግ እንዳለብን ልናውቅ ይገባል ማለት ነው፡፡
በተለይ ለሴቶች ሸንቀጥ ብሎ እና አምሮ መታየት ከዘመኑ ጋር እንደመራመድም ይቆጠራል፡፡ ለምሳሌ ያህል ቦርጭን ለማጥፋት መሰራት ያለባቸው የሰውነት እንቅስቃሴዎች በተለያየ መንገድ ከፋፍለን ልናያቸው እንችላለን፡፡

ለሆድ ከሚሰሩ የስፖርት አይነቶች ውስጥ አንዱ ወለል ላይ በጀርባ በመተኛት እግርን በቀስታ ወደ ላይ በማንሳት እንዲሁም በቀስታ ወደ ነበረበት በመመለስ የሚሰራ የስፖርት አይነት ሲሆን ይህም ለታችኛው የሆዳችን ክፍል የሚሰራ ነው፡፡ ይህ የስፖርት አይነት የሆዳችን ጡንቻ ለረዥም ጊዜ ተሰብስቦ እንዲቆይ ይረዳናል፡፡

ሌላኛው የሆድ ስፖርት አይነት ‹ሳይክል› የምንለው ሲሆን ይህንንም ለመስራት በጀርባችን በወለል ላይ በመተኛት ከዚያም አንደኛውን እግራችንን ወደ ላይ በማንሳት ሌላኛውን እግራችን በማጠፍ እና ወደ ደረታችን በማስጠጋት እየቀያየርን የምንሰራው የስፖርት አይነት ነው፡፡ ይህንን ስፖርት ቢያንስ ለአስር ጊዜ ያህል ደጋግመን መስራት ይኖርብናል፡፡

ከላይ ከገለፅናቸው የስፖርት አይነቶች በተጨማሪ በእንግሊዝኛው (Set up) የሚባለው የስፖርት አይነት ሌላው የሆድ ስፖርት ሲሆን ይህንንም ለመስራት በመጀመሪያ በጀርባችን መሬት ላይ እንተኛለን፡፡ በመቀጠልም ከወገባችን በላይ ያለውን የሰውነታችንን ክፍል ቀና በማድረግ እና እግራችንን እንደዚሁ ቀና በማድረግ የምንሰራው ስፖርት ነው፡፡ ይህም በቀጥታ ለሆድ የሚሰራ ስፖርት በመሆኑ ለውጡን በአጭር ጊዜ ማወቅ እንችላለን፡፡

ከእነዚህ የስፖርት አይነቶች በተጨማሪ ለሆድ እንዲሁም ለእግር የሚሰሩትን የስፖርት አይነቶች እንጨምርላችሁ፡፡

ለዚህ ከሚረዱ የስፖርት አይነቶች ውስጥ አንዱ በጎን በመተኛት እና እግርን በማንሳት የሚሰራ ሲሆን ይህን ስፖርት ለመስራት በመጀመሪያ በጎናችን በመተኛት እንዲሁም ግራ እጃችንን አጥፈን በመንተራስ እና የቀኝ እጃችንን ደግሞ በመሬት ላይ በማሳረፍ የሚሰራ ነው፡፡ እግራችንን እኩል ማነባበር ይኖርብናል፡፡

በመቀጠልም ሌላውን ሰውነታችንን ክፍል ሳናንቀሳቅስ በቀስታ የቀኝ እግራችንን እስከምንችለው ከፍታ ድረስ በማንሳት ለተወሰኑ ደቂቃዎች ባለበት አቆይተን በቀስታ መመለስ ነው፡፡

በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው እና ለሆድ እንዲሁም ለእግር የሚሰራው የስፖርት አይነት በእንግሊዝኛው ክላምሼል የምንለው ሲሆን ይህ የስፖርት አይነት የሚሰራው እንደ መጀመሪያው የስፖርት አይነት በጎናችን በመተኛት ቀጥሎም ጉልበታችንን 45 ዲግሪ በማጠፍ ሲሆን የቀኝ እግራችንን የግራ እግራችን ላይ በማነባበር የሚሰራ ነው፡፡ በመቀጠልም የግራ እግራችንን ባለበት ሆኖ የቀኝ እግራችንን በቀስታ እስመክንችለው ከፍታ ድረስ ከፍ በማድረግ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ማቆየትና ወደ ቦታው በቀስታ በመመለስ የሚሰራ የስፖርት አይነት ነው፡፡ ይህንን በድጋሚ በቀኝ ጎናችን በመተኛት መድገም እንችላለን፡፡
ሶስተኛው የስፖርት አይነት ደግሞ ሂፕ ሬስ ወይም በዳሌ አካባቢ የሚሰራ ስፖርት ሲሆን ይህንንም ለመስራት በመጀመሪያ በወለል ላይ በጀርባችን በመተኛት በመቀጠልም ጉልበታችንን እኩል በማጠፍና በመዘርጋት የሚሰራ ስፖርት ነው፡፡

በመቀጠልም ከትከሻችን እስከ ጉልበታችን ድረስ ያለውን አካላችንን በቀስታ ከፍ በማድረግ ቀጥ ያለ መስመር በመስራት ለተወሰኑ ደቂቃዎች መቆየትና ቀስ ብለን ወደ ቦታችን በመመለስ ይህንኑ በተደጋጋሚ መስራት፡፡ በአራተኛ ደረጃ የተቀመጠው የሆድ ስፖርት አይነት ክሮስ ቦዲ ማውንቴን ክላይምበር (Cross body mountain climber) ሲሆን ይህንን ስፖርት ለመስራት በመጀመሪያ ሁለቱ እጆቻችንን መሬት ላይ በማሳረፍ ቀጥሎም እግራችንን ወደኋላ በመዘርጋት ቀጥ አድርገን ፑሽ አፕ በምንለው የስፖርት አይነት ሰውነታችንን በማዘጋጀት እጃችን ካለበት ሳይንቀሳቀስ የቀኝ ጉልበታችንን በማጠፍ ወደ ግራ ትከሻችን በማስጠጋት እንዲሁም የቀኝ እግራችንን ወደ ቦታው በመመለስ የግራ ጉልበታችንን በማጠፍ ወደ ቀኝ ትከሻችን ማስጠጋት ይኖርብናል፡፡ ይህንንም በተደጋጋሚ መስራት ይኖርብናል፡፡

ከላይ የዘረዘርናቸው የስፖርት አይነቶች በተደጋጋሚ እና በአንድ ጊዜ እየቀያየርን መስራት የምንችላቸው ስፖርት አይነቶች ሲሆኑ በአጭር ጊዜ ለውጥ ልናገኝባቸው እንችላለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ቀለል ያሉ እና በየትኛውም ቦታ ልንሰራቸው የምንችላቸው ስፖርቶች ስለሆኑ በተከታታይ ሳናቋርጥ መከወን ይኖርብናል ሲል ውመንስ ሄልዝ የተባለው መፅሔት ያሳስባል፡፡


(የሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ) ወደ ሃገር ቤት ሲኖዶስ እንቀላቀል የሚለው ወገን ለፍርድ ቤት ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ ሆነ

$
0
0

debereselam Minnesota
ከሰይፉ በላይ

ለረዥም ጊዜያት ሲያነጋግር የቆየው የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ እንደነበረው በገለልተኛነቱ ይቆይ ወይም ወደ ሃገር ቤቱ ሲኖዶስ ይቀላቀል የሚለው ጉዳይ ምላሽ ሊያገኝ ሰዓታት በቀሩት በዚህ ሰዓት፤ ወደ ሃገር ቤቱ ሲኖዶስ እንቀላቀል ከሚለውና ቤተክርስቲያኑን በጌታ ትንሣኤ ቀን ረግጠው ከወጡት ወገኖች የተወከለችው ጠበቃ የፊታችን እሁድ ሜይ 11 ቀን 2014 እንዲደረግ የተወሰነውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲታገድ ለፍርድ ቤት ያቀረበችው ጥያቄ ውድቅ ሆነ።

ወደ ሃገር ቤቱ ሲኖዶስ እንዲቀላቀል ከሚፈልገው ወገን የተወከለችው ጠበቃ ምርጫው ሊደረግ 11ኛው ሰዓት በቀረው ሰዓት ላይ እንዲህ ያለውን ጥያቄ ማቅረቧ ብዙዎችን አስገርሟል።

በዚህም መሠረት ወደ ሃገር ቤት ሲኖዶስ እንቀላቀል የሚለው ወገን በጠበቃው አማካኝነት ያቀረበው አቤቱታ ውድቅ በመደረጉ የፊታችን እሁድ የደብረ ሰላም መድሃኔዓለም ምርጫ በታቀደው መሠረት ይካሄዳል። ለሰላም እና ለአንድነት የቆሙ ምዕመናን ሕዝብ በእሁዱ ምርጫ እንዲሳተፍና ቤተክርስቲያኒቱን እንዲያድን በተለያዩ መንገዶች እየበተነ ያለው ፍላየር የሚከተለው ነው።

ምናባዊ ቃለምልልስ ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር

$
0
0

meles zenawi
ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር ው/ልደታቸውን አስመልክቶ የተደረገ ምናባዊ ቃለ ምልልስ

ልማጠኛ (ልማታዊ ጋዜጠኛ)፡-
እሺ በቅድሚያ ጊዜዎን ሰውተው ስለውልደትዎ ለማውጋት እዚህ ያለሁበት ምናባዊ ስቱዲዎ ድረስ በመንፈስ ስለተገኙልኝ በፌስቡክና በመላው የሽሙጥ ማህበረሰብ ስም ለማመስገን እወዳለሁ፡፡ እስቲ ያሉበትን ሁኔታ በአጭሩ ቢያስረዱ፡፡

መለስ፡-
ያለሁበት ሁኔታ ግልጽ ነው፡፡ በምድር ሳለሁ ለሰራሁት ስራ ጥሩም ሆነ መጥፎ ሂሳቤን በሙሉ ኦዲት እያደረኩ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ እዚህ እያንዳንዷ ነገር ሁሉ የራሷ አካውንት አላት፡፡ ያው ባላንሴ ዴቢት እና ላያቢሊቲ ብቻ ሆኖብኝ መጨነቄን ልትገምት ትችላለህ፡፡ ብዙ አታስገባኝ ወደሱ፡፡

ልማጠኛ፡-
እሺ ይተዉት እሱን፡፡ ዛሬ የልደትዎ ቀን ነው፡፡ በእርስዎ መወለድ ዓለም ምን ተጠቅማለች ብለው ያስባሉ፡፡ ምንስ ጉዳት ተከስቷል?

መለስ፡-
ዌል እንግዲህ በእኔ መወለድ ብዙ ጥቅም እና ጥቂት ጉዳቶች መከሰታቸውን በመረጃ ብቻ ሳይሆን በማስረጃም ጭምር ማሳየት እችላለሁ፡፡ ግን አንተ ማወቅ የፈለግከው ከልጅነቴ ጀምሮ የነበረውን ነው ወይስ ስልጣን ላይ በአሚር ሙጫ ከተጣበቅኩ በኋላ ያለውን ጊዜ ብቻ ነው?

ልማጠኛ፡-
የወጣትነትዎና የትግሉን ዘመን ለጊዜው ይተዉት፡፡ ብዙም የሚያወያይ ነገር ላይኖረው ይችላል፡፡ በይበልጥ የጠቅላይ ሚኒስትርነት ጊዜዎትን ነው ማወቅ የፈለግኩት፡፡

መለስ፡-
ይሁንልህ፡፡ እኔ ተወልጄና አድጌ ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆንኩ ጀምሮ በርካታ ጥቅሞች ተገኝተዋል፡፡ ለምሳሌ ለኢትዮጵያ ህዝብ ከዋልኩት ውለታዎች አንዱ በቀን ሶስት ጊዜ መብላት የሚባለውን ነገር በወሬ ደረጃ ማስተዋወቄ ነው፡፡ እምልህ… ተግባር ሌላ ነገር ነው፡፡ ግን እውን ባይሆንም እንኳ ሶስቴ የመብላትን ተስፋ ለድሆች መስጠት ቀላል ነገር አይደለም፡፡ ሶስት ቀን ባይችሉ እንኳ በሶስት ቀን አንዴ መብላት ላይከብዳቸው ይችላል፡፡ ኢንፋክት ከእኔ ጠቅላይነት በኋላ በአንድ ጊዜ ከ5 ሚሊየን ሰው በላይ ሲራብ አልታየም፡፡ ሁሌም ከ5 ሚሊየን እስከ 4 ሚሊየን 999 ሺ 999 ሰው ብቻ ነው ሲራብ የነበረው፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ እኔ ለፍቼና ላቤን አንጠፍጥፌ፣ ድንቅ የሚባል የኢኮኖሚ እውቀቴን በመጠቀም እንዲከሰት ባደረግኩት የኑሮ ሁኔታ የሰዎች የምግብ አምሮት እንዲጨምር አድርጌያለሁ፡፡ አፒታይት ማለቴ ነው፡፡ ዱሮኮ ስጋ በሳምንት ሶስቴ ወይ ሁለቴ ይበላ ነበር፡፡ ማንም አይናፍቀውም፡፡ አሁን ግን የፍቅር ዘፈን ተዘፍኖለት ‹‹ቁርጤ ቁርጠቴ›› ተዘምሮለት ነው የሚገኘው፤ በክብር.. ለዚያውም ደሞዝ ተጠብቆ! ህዝብ ይንቃቸው የነበሩት ጣፊያና አንጀት እንኳ ዛሬ አዲሳባ ላይ መበላት መጀመራቸው የኔ ውለታ ነው፡፡ ሸኾና ራሱ በእነሱ ቀንቶ ‹‹እኔስ መቼ ነው የምብበላው?›› የሚል ንቅናቄ ሊጀምር መሆኑን ሰምቻለሁ፡፡

ልማጠኛ፡-
ለጊዜው አገሪቱ ውስጥ ያለው ህጋዊ ንቅናቄ የ‹‹ቐ›› ንቅናቄም ብቻ ነው ክቡርነትዎ፡፡ ለማንኛውም ይቀጥሉ እስቲ!

መለስ፡-
መልካም፡፡ እንደውም የስጋ ነገር ሲነሳ በግ ትዝ አለኝ፡፡ ዱሮ ትዝ ይልሀል በየሰፈሩ በአምስት ብር በሚቆረጥ ሎተሪ በግ እንደሽልማት ይደርስ ነበር፡፡ እንደውም ትዝ ይለኛል ገና ምኒሊክ ቤተ መንግስት እንደገባን አንዱ የበግ ሎተሪ ሲያዞር አዜብ አግኝታው የእኔ 6ሺ ብር ደሞዝ እስኪደርስ ከጓደኞቿ ተበድራ ገዝታ ነበር አልደረሳትም እንጂ፡፡ እሱን የበግ ሎተሪ ደርግ ነው ያስጀመረው ታውቅ ከሆነ፡፡ ያው ደርግ በበግ ሎተሪ አስጀመረ… እኔ ደግሞ በኢኮኖሚ ፖሊሲዬ በበዓል እንኳ የሚታረደውን በግ ሎተሪ አደረግኩት፡፡ አሁንኮ በግ ገዝቶ ማረድ ሎተሪ እንደማሸነፍ ሆኗል አሉ፡፡ በግ ተገዝቶ ሲገባ ሰፈር ውስጥ እንደሙሽራ ተጨብጭቦለት የሚገባ መሆኑን ሰምቻለሁ፡፡ በዚህ ታዲያ ሌላው ቢቀር የበግ መብት ተቆርቋሪዎች ሁሉ ሳይደሰቱ ይቀራሉ ብለህ ነው? እንግዲህ የኔ ሌጋሲ ነው ይሄ!

ስኳርስ ቢሆን! ከእኔ በፊት የተናቀና በየወረቀቱ ተጠቅልሎ የሚሸጥ ‹‹ርካሽ›› ነገር አልነበረም እንዴ? ታምራት ላይኔ እንኳ ገና እንደገባን ስንቴ ሲልሰው ነበር! ዘይትም ቢሆን ያምስት አምስት ነበር ዱሮ፡፡ ዛሬ እቴ … እኔ ልመስገን እንጂ ስኳርና ዘይት ትንሽ ጠፋ ካለ ለትዳር ሽማግሌ እንደሚላከው ለቀበሌ ካድሬ አማላጅ ተልኮ ተለምኖ ነው በክብር በሰልፍ ቀብረር ብሎ የሚመጣው፡፡ አንዳንዱ እንደውም እንደዱሮው ትዳር ጠለፋ ምናምን ሁላ ይሞካክር ነበር፡፡

ልማጠኛ፡-
ክቡር ጠቅላይ… እስቲ ምግቡን ይተዉት ለጊዜው፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነኝ፡፡ ዜርፎር ስጋ ራሱ ከበላሁ ትንሽ ቆይቻለሁ፡፡ በጎመን ብዛት ቬጂቴሪያን ከሆንን ቆየን፡፡ አምሮቴን ከሚቀሰቅሱ ወደሌሎች ውለታዎችዎ ብናልፍ፡፡

መለስ፡-
ኦኬ! ከዩኒቨርሲቲ ሳንርቅ እንይ፡፡ ኮብልስቶን በማን ዘመን ነው ክብር ያገኘችው? ማንንም ጠይቅ! ወላ አውሮፓ ወላ አሜሪካ የከፍተኛ ትምህርት ቀመስ ባልሆኑ ሰዎች እጅ ስንት ዘመን ቅኝ ተገዝታለች? እኔ አይደለሁም እንዴ በዩኒቨርሲቲ ምሩቃን እጅ ማእረግ አግኝታ እንድትስሰራ ያደረኳት? ‹‹የተማረ ይፍለጠኝ›› ብላ የተረተችው የኮብልስተን ንግስት ለዚህ ምስክር መሆን ትችላለች፡፡

ሌላው ደግሞ ዱሮ ኤለመንታሪ ትምህርት ቤት በመደዳ ግርፊያ የሚባል ትዝታ ነበረን፡፡ ሰክሮ የመጣ አስተማሪ ረበሻችሁ ብሎ በመደዳ ይገርፍ ነበር ተማሪውን፡፡ ያ የተማሪዎች ቋሚና የሚናፈቅ ትዝታ ሆኖ አልፎ ነበር፡፡ ያንን ትዝታ ለናፈቃቸው ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በፓዮኔርነት አስተዋውቄያለሁ፡፡ አንድ ተቃውሞ ሲያነሱ ፌደራል ገብቶ በመደዳ የቀጠቀጣቸው በእኔ ዘመን ብቻ ነው፡፡ በዚህም የዱሮ ትዝታቸውን የማመንዠግ እድል አግኝተዋል፡፡ በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎችም የናፈቃቸውንና በፊልም ብቻ ይሰሙት የነበረውን የጥይት ድምጽ እንዲሰሙ አድርገናል፡፡ ቀላል ነው እንዴ ይሄ? እነሱምኮ ትንሽ አክሽን ትሪለር ምናምን ነገር ያስፈልጋቸዋል! ይኸው በቅርቡ እንኳ በአምቦና በሌሎችም ከተሞች የኦሮሚያ ከተሞች ተማሪዎችን የዚህ በረከት ተቋዳሽ ማድረግ የተቻለው በእኔ ሌጋሲ ነው፡፡ ስንቱ ተቀነጨለ በግርግር፡፡

ልማጠኛ፡-
እስቲ አሁን ደግሞ ወደተቋማት ይምጡልኝ፡፡ ተቋማት በእርስዎ ዘመን ምን ተጠቅመዋል ብለው ያስባሉ?

መለስ፡-
ብዙ ተጠቅመዋል፡፡ ለምሳሌ ማረሚያ ቤት ተቋምን ውሰድ፡፡ ወላ ቃሊቲ ወላ ቅሊንጦ ዱሮ ከሞላ ጎደል የወንጀለኞች ቦታ ነበር፡፡ አሁን ግን ለቦታው መሰጠት ከሚገባው ክብር አንጻር ምርጥ ምርጥ የሚባሉ ሰዎችን ከየአቅጣጫው በመምረጥ እንዲታሰሩበት አድርገናል፡፡ ዛሬኮ እስር ቤት ያልገባ የለም፡፡ እንደውም ‹‹የጀግና ቤቱ እስር ቤት ነው›› የሚል ተረት ሁላ ተጀምሯል ሰምተህ ከሆነ፡፡ እስር ቤት በቅርብ ታሪካችን እንዲህ አይነት ክብር አግኝቶ አያውቅም፡፡ ወላ ፖለቲከኛ፣ ወላ ተቃዋሚ ፓርቲ፣ ወላ ጋዜጠኛ፣ ወላ የሃይማኖት አባቶች የት ነው ያሉት ዛሬ? እስር ቤት አይደለም እንዴ? ኦፍኮርስ! ሌላው ቀርቶ በርካታ ባለስልጣናት እንኳ እየገቡ ነው በስኳር ጦስ፡፡

ደግሞ እስር ቤት ብቻ አይምሰልህ ክብር ያገኘው፡፡ አግአዚ ክፍለ ጦርስ ቢሆን አልተከበረም እንዴ? ዱሮ ማን ያውቀው ነበር? እኔ ነኝ ከወደቀበት አንስቼ በሺዎች በሚቆጠሩ እናቶችና አባቶች አፍ ያስገባሁት፡፡ በእርግማን መሆኑን አትይ ዋናው መነሳቱና ዝናው መናኘቱ ነው፡፡ ዱሮ ክፍለጦሩ ጥይት እንኳ የሚተኩሰው ልምምድ ላይ ብቻ ነበር፡፡ አሁን ግን ክብር ተሰጥቶት የትም ቦታ ተቃውሞ ላይ ቀይ ኮፍያውን ለብሶ ከች ይላል፡፡ ‹‹ተኩስ!›› ሲባል ብቻ በስናይፐር መቀንደብ ነው! ‹‹ቋ! ጧ! ጯ!›› ያረጋል እያነጣጠረ! ህጻን መምረጥ የለ አዋቂ! ይህን የመሰለ ዝና ታዲያ ከየት ነው የሚመጣው? አንድን ተራ ክፍለጦር ከሂትለር የ‹‹ፖግሮም›› ፖሊስ እኩል ዝና ማቀዳጀት ቀላል ነው እንዴ?

ለማእከላዊ ምርመራ ጣቢያም ሆነ የአገር ፍቅር ለሚለበልባቸው ገራፊዎቹ የዋልኩት ውለታም የሚረሳ አይደለም፡፡ በደርግ ዘመንኮ ገራፊዎች በግልጽ ስለሚገርፉ ብዙ ወቀሳ ይደርስባቸው ነበር፡፡ በእኔ ዘመን ግን ህጋዊ ሽፋንና ጠለላ አግኝተዋል፡፡ የጸረ ሽብር ህጉ ተመቻችቶላቸዋል፡፡ የግርፋት ጊዜያቸው አጭር ነበር በፊት፡፡ እኔ ነኝ ከብዙ ጥረት በኋላ በፍርድ ቤት ፈቃድ ለ4 ወራት ያክል በነጻነት መግረፍ እንዲችሉ ያመቻቸሁት፡፡ ትቢተኛ ዳኞችን እንኳ እኔ ነኝ ‹‹እንዳላየ ሆናችሁ እለፏቸው፤ ተባበሯቸው፤ ህጋዊ ሂደቱን አሳልጡላቸው›› ብዬ አስጠንቅቄ ቀና ብለው እንዳያዩዋቸው ያደረኩት፡፡ ማንም ተራ ዳኛኮ የማእከላዊ ገራፊን እንደዱሮው ሊናገረው አይችልም፡፡ መገልመጥ ቀርቶ በዓይኑ ቂጥ ሊያየው አይችልም፡፡ ተቋማዊ መከባበሩ ሰፍኗል፡፡ በዚህ ምን ያክል እንደሚደሰቱ ገምት፡፡ ተቋማዊ ነጻነት ያለውን አስፈላጊነት የሚረዱ ሁሉ ሲያመሰግኑኝ ይኖራሉ በዚህ!

ልማጠኛ፡-
እስቲ ለህዝቡ የዋሉለት ካለም ቢጨምሩልን፡፡

መለስ፡-
ለሀዝቡ በዋነኝነት ዋልኩት ውለታ ለአገሩ መሞት እንዲችል ማድረጌ ነው፡፡ ይሄ ትልቅ ክብር ነው ያው፡፡ የተለያዩ ጭቆናዎችን በማድረግ ሰዎች በግልም በቡድንም ለትግል እንዲነሳሱና በሂደቱም ለአገራቸው ነፍሳቸውን እንዲሰጡ አመቻችተንላቸዋል፡፡ ይሄ ደብል ጥቅም ነው ያለው፡፡ ለህዝቡም ለአገር የመሞትን ክብር እንደሚያቀዳጅ ሁሉ ለፌደራልና አግአዚም ነጻ የሰው ዒላማ ይሰጣቸዋል፡፡ ውትድርና ስትሰለጥን ያው መተኮስ ሊያምርህ ይችላል፡፡ ይህ አምሮት ባለፈው ጎንደር ላይ አንዱ ፌደራል አስራ ምናምን ሰው እንደገደለው በህገወጥ መልኩ ከሚተገበር የሰላማዊ ተቃዋሚ አጋጣሚ ሲገኝ እንደ97ቱ፣ እንደአኙዋኩ፣ እንደጋምቤላው፣ እንደደሴው፣ እንደጎንደሩና ትግራዩ፣ እንደሱማሌ ክልሉ፣ እንደአሳሳውና ኮፈሌው፣ እንደአምቦው ወዘተ በህጋዊ መልኩ ቢተገበር ይሻላል ከሚል መነሻ ነው የተነሳነው፡፡

ሌሎችንም አጋጣሚዎችን ፈጥረናል፡፡ ለምሳሌ በባድመ ጉዳይ እንደቀልድ ከኢሳያስ ጋር በርጫ ላይ የፈጠርናትን ጨዋታ የምር አድርገናት ‹‹ለምን ፉል ፍሌጅድ ጦርነት አድርገነው በኋላ አንሸማገልም›› በሚል ተነጋግረን በኢትዮጵያ በኩል ወደ 70 ሺ ሰው አካባቢ ለእናት አገሩ የመሞት እድል ፈጥረናል፡፡ መሬቱን ያው ጦርነቱ ሲያልቅ መልሰንለታል ለኢሴ፡፡ ይህ ለህዝብ ከዋልኳቸው ውለታዎች አንዱ ነው፡፡

ልማጠኛ፡-
ብዙ ውለታ ነው የጠቀሱልኝ፡፡ ይህ ሁሉ ውለታ በእርስዎ ሞት መቋረጡ በእርግጥም አሳዛኝ ነው፡፡ እንዳልኩዎት…

መለስ፡-
ኖ! ኖ! አትሳሳት! እኔ በበሞቴ የተቋረጠ ውለታ የለም! አሁንምኮ እነዚህ ነገሮች ቀጥለዋል፡፡ በኔ ሌጋሲ አይደለ እንዴ አገር እየተገዛ ያለው! እነ ሃይለማሪያም ደሳለኝ እና ግርማ ወልደጊዮርጊስ ሁሉ በእኔ ሌጋሲ አይደል እንዴ እየተንደላቀቁ ያሉት?

ልማጠኛ፡-
ሁለቱ አይለያዩም ጌታዬ? አቶ ሐይለማርያምኮ ጠቅላይ ሚኒ…..

መለስ፡-
አይለያዩም ባክህ! ጆብ ስፔሲፊኬሽናቸው ሁሉ አንድ ነው!

ልማጠኛ፡-
በመጨረሻ የሚጨምሩት ነገር ካለ እድሉን ልስጥዎት፡፡

መለስ፡-
ብዙ የምለው እንኳ የለኝም፡፡ ህዝቡን ብቻ ማመስገን ነው የምፈልገው፡፡ እንደአንድ ጣኦት ልመለክ የምችልበትን እድል ለማመቻቸት ለሚደክሙት ካድሬዎችም ሰላምታ ማቅረብ እፈልጋለሁ፡፡ እዚህ ፌስቡክ ላይም የተወሰኑት እየሰሩት ያለውንም ስራ አይቻለሁ፡፡ ምንም አይልም፡፡ ትንሽ ብቻ አንዳንዴ እያበዙት ጥርስ እያስነከሱብኝና የማንም መቀለጃ እያረጉኝ ከመሆኑ በስተቀር ጥሩ እየለፉ ነው፡፡ ምኞታቸው ተሳክቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ እመለካለሁ የሚል ተስፋ ባላደርግም እታገሳለሁ፡፡ ይብቃን ለዛሬ፡፡

ውይ ረስቼው! ሜሮን ጌትነትንም ሰላም በልልኝ በናትህ፡፡ እሷ ልጅ ጥያቄና መልስ ውድድር ላይ በሌጋሲዬ ስም ያልተመለሰ ጥያቄ ሁሉ ነጥብ ትሰጣለች አሉ! ለካ ለልማታዊ አርቲስቶችም ብዙ ውለታ ውያለሁና!

ልማጠኛ፡-
አመሰግናለሁ አቶ መለስ!

መለስ፡- አመሰግናለሁ! ሙድህ ከጣመኝ ወደፊትም ብቅ እያልኩ ቃለ መጠይቅ ልሰጥህ እችላለሁ!
===================================

(ማሳሰቢያ፡- ይሄ ቃለ መጠይቅ ምናባዊ ነው፡፡ ዓላማው መለስ በስልጣኑ ከሰጠው ጥቅም ይልቅ በጨቋኝ ስርአቱ ያዘነበብን ጉዳት በጣም እንደሚከፋ ማሳየት ነው፡፡ መለስ አንዳችም ጥሩ ነገር አልሰራም ለማለት አይደለም፡፡ ጥሩ ነገሩ በ99.6 በመቶ ተጋኖ በኢቲቪና አንዳንዴም በፌስቡክ አሰልችቶናል፡፡ ጭቆና የቀደመ በጎ ስራን እንደእሳት ይበላል፤ ለዚህ አትጠራጠሩ፡፡ የመለስ ልደት በዓል ለሆነላችሁ የስርአቱ ተጠቃሚዎችና ቅልብ ካድሬዎች ደግሞ ሙት በመውቀስ ጽንፍ ረግጬ ከሆነ ይቅርታችሁን እለምናለሁ፡፡ አንድ ቀን እንደምትወለዱ ተስፋ በማድረግ! መልካም ልደት!)

‹‹ያለምንም ደም››
‹‹ሌጋሲው ይቅደም!›› ቂቂቂ

በምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ፤ የአጋዚ ጦር አካባቢውን ወሮታል

$
0
0

gimbi welega
አሁን ለዘ-ሐበሻ በደረሰ መረጃ መሠረት፦

በምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ የአዲስ አበባን አዲሱን ማስተር ፕላን በመቃወምና ሰሞኑን በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በአጋዚ ወታደሮች የተገደሉ ወገኖችን ለማሰብና ገዳዮች ለፍርድ እንዲቀርቡ እየጠየቁ ያሉ ሰዎች አደባባይ የወጡ ሲሆን ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ባሉበት ወቅት በአጋዚ እና በፌደራል ፖሊስ መከበባቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመለከተ።

የአጋዚ ጦር በጊምቢ ወረዳ የተከሰተውን የተቃውሞ ሰልፍ ለማብረድ የኃይል እርምጃ እንደወሰደ የገለጹት የዘ-ሐበሻ ሰዎች ምን ያህል ሰዎች እንደተጎዱ ያረጋገጥነው ነገር የለም ብለዋል።

ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን እንመለሳለን።

የሄንሪ ቀመር በአንፊልድ ሊቨርፑል (ልዩ ትንታኔ)

$
0
0

የትልቅነት ማዕረጉን ተገፍቶ የቆየው ሊቨርፑል ወደ ክብሩ እየተመለሰ መሆኑን የዘንድሮ ስኬታማ ግስጋሴው ይጠቀላል፡፡ ለቀዮቹ ጥንካሬ ብሬንዳን ሮጀርስ ትልቅ አድናቆት ቢገባቸውም የክለቡ የሽግግር ጉዞ ዋናው ቀያሽ ጆን ሄንሪ ናቸው፡፡ አሜሪካዊው በአዲስ አስተሳሰቦች ስኬትን እንዴት ማምጣት እንደሚቻል የተገነዘቡ ናቸው፡፡ ይህንን አቅማቸውን በቢዝነሱ እና በስፖርቱ እንዴት መጠቀም እንዳለባቸውም ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ አዲስ እና የተለዩ ሀሳቦችን እያፈለቁ ውድቀትን ሳይፈሩ ያሰቡትን ይተገብራሉ፡፡
ሄንሪ በአሜሪካ ቦተን ሬድ ሶክስ የተሰኘውን ክለብ በባለቤትነት ሲረከቡ በቤዝቦል ስፖት እጅግ ስኬታማ ተብሎ ይጠቀስ ከነበረው ኒው ዮርክ ያንኪስ ጋር የነበረውን ሰፊ ልዩነት ለማጥበብ አንድ የተለየ ሀሳብ ማፍለቅ ነበረባቸው፡፡ የአሜሪካው ኦክላንድ አትሌቲክ በቤዝቦል ስፖርት ራሱን መልሶ ለማጠናከር ጥናት ማድረጉን ያውቁት ሄንሪ በተመሳሳይ ሬድ ሶክስን መልሰው ለመገንባት ሊጠቀሙበት ሲንቀሳቀሱ ማንም አልፈቀደማቸውም፡፡
የውድቀት ፍርሃት’
liverpool
ሊቨርፑል በሮጀርስ ስር ሲሰለጥን አንዱ የጠቀመው ከውድቀት ፍርሃት ነፃ መሆኑ ነው፡፡ ይህ ያለመፍራት መንፈስ ደግሞ ከክለቡ አናት የመነጨ ነው፡፡ ሄንሪ እና የፌንዌይ ስፖርትስ ግሩፕ (FSG) ቀደም ሲል ስህተቶች ሰርተዋል፡፡ ነገር ግን በስህተቶቻቸው እየተማሩ ሊቨርፑል ከሌሎች ተቀናቃኞቹ ጋር ያለውን ልዩነት ለማጥበብ ሞክረዋል፡፡ የአሁኑ የሊቨርፑል ትልቅ የጥንካሬ ባህርይ የክለቡን የስልጣን ተዋረድ ተጠቅሞ ከላይ የወረደ ነው፡፡
ሊቨርፑል የተለየ ነገር መሞከር ለመፈለጉ አንዱ ማስረጃ ዳሚዬን ኮሞሊን መሾሙ ነው፡፡ ሆኖም ይህ እንዳልሰራ ሲመለከቱ በቶሎ ሀሳባቸውን አረሙ፡፡ በዝውውር ገበያ ላይ አብዝቶ መሳተፍ ስኬትን እንደማያረጋግጥ ተገነዘቡ፡፡ ስለዚህ ሌላ አይነት ቀመር መሞከር ነበረባቸው፡፡
ሄንሪ ሁልጊዜም በሊቨርፑል ሰፋ አድርገው ማሰብ እና ጠቅለል ያለ ስዕል መመልከት ይፈልጋሉ፡፡ ሰውዬው ለሚፈጠሩ አደጋዎች መፍት ለመስጠት እጃቸውን አጣምረው የሚጠባበቁ ሳይሆኑ እያንዳንዷን እርምጃ አስቀድመው አስበው በስትራቴጂ መሄድ የሚመርጡ ናቸው፡፡ ደጋፊዎች እንደ ትልቅ ስህተት የሚመለከቱትን እርሳቸው የስኬታቸው ግስጋሴ ምስክር አድርገው በበጎ ያዩታል፡፡ በእግርኳስ የተለዩ እና አዳዲስ አስተሳሰቦችን ማራመድ ከባድ ነው፡፡ ምክንያቱም ደጋፊዎች ምንም አይነት ውድቀትን አይታገሱም፡፡ ሆኖም ከውድቀቶች እየተማሩ እንጂ በቀጥት ስኬት ጋር አይደርስም፡፡
አለማችን ካፈራቻቸው ድንቅ እና ታላላቅ ስፖርተኞች አንዱ የሆነው ማይክል ጆርዳን በአንድ ወቅት ይህንን ብሏል፡፡ ‹‹በህይወት ዘመኔ ደጋግሜ ውድቀትን ተጎንጭቻለሁ፡፡ የተሰካልኝም ለዚህ ነው፡፡ ሄንሪ እና FSG ለፈጠራ በሰላም አዕምሮ ቢዝነስን ማሳደግን ያውቁበታል፡፡ ሊቨርፑልን እና ሬድ ሶክስን እያስተዳደሩ ያሉትም በዚህ መንገድ ነው›› ሄንሪ ይህንን ቀመር ወደ ውጤት ለማድረስ እና ሊቨርፑልን መልሰው ሃያል ለማድረግ የተከተሏቸውን መንገዶች መቃኘት እንችላለን፡፡
የሮጀርስ ሹመት
ሄንሪ የሊቨርፑልን ህዳሴ በበላይነት ይምሩ እንጂ ራዕያቸውን የሚጋራ፣ አዳዲስ ሀሳቦችን በመሞከር የሚያምን እንዲሁም ቡድኑን ሜዳ ላይ የሚመራ ሰው ያስፈልጋቸው ነበር፡፡ ሮጀርስ ይህንን ሁሉ በውስጣቸው የያዙ እውነተኛ መሪ መሆናቸውን አሜሪካዊው አመኑበት፡፡ ወጣቱ አሰልጣኝ ሜዳ ላይም አዳዲስ ሃሳቦችን እየተጠቀመ ለስኬት እንደሚሰራ እርግጠኛ ሆኑበት፡፡ ሄንሪ ሮጀርስን ሲሾሙ የእግርኳስ ፍልስፍናቸውንም እንዲያራምዱ ፈቀዱላቸው፡፡ ሮጀርስ ሄንሪን አላሳፈሩም፡፡ በተለይ መንገድ ሊቨርፑልን ውጤታማ አደረጉት፡፡ ሰውየው በቡድኑ የተለዩ ሁኔታዎችን ፈጥረዋል፡፡ የሊቨርፑል ተጨዋቾች ለግጥሚያ በአዕምሯቸው ዝግጁ እንዲሀኑ በዓለም ላይ የላቁ ከሚባሉት የስፖት ስነ ልቦና ባለሙያዎች አንዱን አስቀጥረዋል፡፡ ፕሮፌሰሩ በቀጥታ ቡድኑ ላይ የፈጠሩት ተፅዕኖ በጥናት ባይረጋገጥም የዘንድሮው የሊቨርፑል ተጨዋች አካላዊ እና አዕምሯዊ ጥንካሬ ግን አስገራሚ ሆኗል፡፡
ሮጀርስ ተጨዋቾቻቸውን ሲያቀናጁም እንደዚሁ የፈጠራ አቅማቸው ይንፀባረቃል፡፡ ከግጥሚያዎች በፊት ሊቨርፑል በየትኛው ጨዋታ ምን አይነት አጨዋወት ይዞ እንደሚቀርብ መገመት ያስቸግራል፡፡ ሮጀርስ የመጠቁ ታክቲክ አዋቂ ተብለው ባይፈረጁም ቡድናቸውን የማይገመት ማድረግን ያውቁበታል፡፡ ዘንድሮ ከቡድኑ የጥንካሬ ሰበቦች አንዱ ይኸው የማይጨበጥ የጨዋታ ስትራቴጂ ይዞ የመገኘት ባህሪዬ ነው፡፡ ይህ የሮጀርስ የፈጠራ ዝንባሌ በሄንሪ ፍላጎት እየተበረታቱ የሚተገብሩት ነው፡፡
የዝውር – ኮሚቴ
የኮሞሊ መምጣት እንደታሰበው ስኬታማ ሆኖ አይገኝ እንጂ ሀሳቡ በራሱ ስህተት አልነበረም፡፡ ሰውየው የተሾሙት በዝውውር ገበያው ሰዎች በቀላሉ ከሚያዩት አልፈው እንዲመለከቱ ነበር፡፡ ሆኖም አሰራሩ ችግር እንደነበረው ለማወቅ የአንዲ ካሮል ግዢ በቂ ነበር፡፡ ሉዊስ ሱአሬዝን የመሰለ ኮከብ በ22 ሚሊዮን ፓውንድ የገዙት ሰው ለቀድሞው የኒውካስል ወጣት ዝውውር 35 ሚሊዮን ፓውንድ እንዲከፍል መስማማታቸውን ማመን ያስቸግራል፡፡
በዚህ የዝውውር ሂደት መቀጠል እንደማይችሉ የተገነዘቡት ሄንሪ በ2012 ክረምት የዝውውር ኮሚቴ አቋቁሙ፡፡ በእርግጥ የኮሚቴ አሰራር አዲስ አልነበረም፡፡ ብዙዎቹ ክለቦች እንዲህ አይነት መዋቅር አላቸው፡፡ የሊቨርፑሉ ኮሚቴ ግን በተለየ መልኩ የተጫዋቾችን ባህላዊ የምልመላ ስርዓት ከስታስቲካዊ ትንታኔዎ ጋር አነፃፅሮ የጋራ ስምምነት ላይ ይደርሳል፡፡ ከኦክላንድ አትሌቲኮ ሞዴል የተቀዳ ሳይሆን አይቀርም ተብሎ የሚገመተው ይህ አሰራር ምናልባት በእግርኳሱ ለቦሩሲያ ዶርትሙንድ የዝውውር ስትራቴጂ ይቀርባል፡፡
ኮሜርሺያል
የአሁኖቹ የሊቨርፑል ባለሀብቶች ከቀድሞዎቹ በተለየ መልኩ ክለቡ በኮሜርሺያል እንዲያድግ የትኛውን አካባቢ ኢላማው ማድረግ እንዳለበት ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ አዳዲሶቹ የክለቡ የቢዝነስ ዲፓርትመንት ሰዎች የሊቨርፑል ገቢ ያሳደጉበት ፍጥነት ያስደንቃል፡፡ ሬድ ሶክስ በFSG ባለቤትነት ስር ከገባ ወዲህ ከኒውዮርክ ያንኪስ ጋር የነበረውን ሰፊ ርቀት ለማጥበብ 90 የሚደርሱ ተጨማሪ የቢቢነስ አጋሮች ጋር በኮንትራት ተጣምሯል፡፡
የአሜሪካዊያኑ አዳዲስ ሃሳቦች ሊቨርፑል ለወደፊቱ የተደላደለ እና አስተማማኝ ፋይናንስ እንዲኖረው የሚያደርጉ ስትራቴጂዎችን ይዘዋል፡፡ በዓለም ዙሪያ እጅግ ከፍተኛ ደጋፊ ያለው የመርሲ ሳይዷ ክለብ መልካም አጋጣሚዎቹን ሁሉ ቀስ በቀስ በመጠቀም የገበያውን ስፋት ወደ ገንዘብ የመቀየር ዕድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ ለጊዜው የሊቨርፑል አጠቃላይ ሂብ ኪሳራ ቢያሳይም የኮሜርሺያል ትርፉ እያደገ ነው፡፡ የክለቡ ኮሜርሲያል ስትራቴጂ ምናልባትም በጥቂት ዓመታት ወስጥ ትርፋማ አድርጎት የቡድኑን ተፎካካሪነትም ከፍ ሊያደርገው ይችላል፡፡ ምናልባትም በፋይናንሱ የበረታው ክለብ በዓለም ላይ አሉ የተባሉ ምርጥ ተጨዋቾችን ወደ አንፊልድ ይስባል፡፡
ስታዲየም
አንፊልድን የማስፋፋቱ ሀሳብ የሚሳካ አይመስልም ነበር፡፡ የሊቨርፑል ከተማ ምክር ቤትም ፈቃድ የመስጠት ምልክት አላሳየም፡፡ ስለዚህ ምናልባትም ክለቡ ይህንን ሀሳቡን ትቶ አዲስ ስታዲየም ለመገንባት ቢያቅድ እንደሚሻል ሲነገር ነበር፡፡ ሄንሪ ወደ እንግሊዝ ከመጡ በኋላ ግን ሁሉም ነገር ተለወጠ፡፡ አንፊልድን የማስፋፋቱ ሀሳብ የሚቻል መስሎ ታየ፡፡ እንዴት?
ይህ የሄንሪ ሁኔታዎችን ‹‹አይቻልም›› ከሚለው አልፎ የመመልከት ባህሪይ ያመጣው ነው፡፡ ለፈጠራ አዕምሮውን ክፍት ያደረገ ሰው ችግሮን ለማለፍ መፍትሄ ይመከታል እንጂ ወደ ኋላ አይመለስም፡፡ አሁን ሊቨርፑል ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚስማማ ስታዲየም እየተመለከተ ነው፡፡ ይህ ስታዲየም አንፊልድ ራሱ ነው፡፡
የFSG ሰዎች ለቦስተኑ ክለባቸውም ተመሳሳይ ዘዴ ተጠቅመዋል፡፡ በዚያም አይቻልም እየተባሉ በተለየ ብልሀት የቤዝቦሉን ክለብ ስታዲየም አግዝፈው ተጠቅመውበታል፡፡ ሰዎቹ ለስኬት አይተኙም፡፡ በሩጫቸው ሁሉ የሚገጥማቸውን ውድቀት ተቀብለው እና ተምረውበት ቀጣዩን እርምጃ ይጀምራሉ፡፡ በሬድ ሶክስ ደጋግሞ ውድቀት ቢጎበኛቸውም በመጨረሻ የስኬቱን ቀርም አግኝተውት በ10 ዓመታት ውስጥ ሶት የWorld Series (የአሜሪካ ቤዝቦል ሻምፒዮና ውድድር) አሸንፈዋል፡፡ አሁን FSG የቀደመ ልምዱን ታጥቆ ሊቨርፑልን በድጋሚ ትልቅ ሊያደርግ ተነስቷል፡፡ እያንዳንዱን እርምጃውንም በጥናት እና በእቅድ ተያይዟል፡፡ አሜሪካዊያኑ ሮጀርስን በአሰልጣኝነት ሲቀጥሩ ሰውየው ከገንዘብ በላይ ጊዜ እንደሚያስፈልገው አውቀዋል፡፡ የአንፊልዱን ክለብ በሶስተኛው ዓመት ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ ሊመልሱ ቃል ይገቡት አሰልጣኝ በሁለተኛ ዓመታቸው ሊቨርፑልን የዋንቻ ተፎካካሪ አድርገውታል፡፡ ከሜዳ ውጪ ደግሞ የክለቡ የኮሜርሺያል ባለሙያዎች የሊቨርፑልን ገበያ እያሰፉ እና የቢቢነስ ሽርኮቻቸውን በቁጥር እያሳደጉ አስገራሚ ግስጋሴ ላይ ናቸው፡፡ የሄንሪ ቀመር እየሰራ ነው፡፡

የሜርሲሳይድ መነቃቃት
በሜርሲ ሳይድ በአይነቱ ልዩ የሆነ መነቃቃት እየታየ ነው፡፡ በዚህ የውድድር ዘመን የሊቨርፑል ከተማዎቹ ሁለት ክለቦች አስገራሚ ብቃት በማሳየት ላይ ናቸው፡፡ የውድድር ዘመኑ ሲጀመር ተሰጥቷቸው ከነበረው ግምት በላይ መሆን ችለዋል፡፡

ከሊቨርፑል ምን ተጠብቆ ነበር?
ሊቨርፑል የውድድር ዘመኑን የጀመረው ቅይጥ የሆነ እምነት እና ግምት ይዞ ነው፡፡ በ2012-13 የውድድር ዘመን ቡድኑ ያስመዘገበው ውጤት የተገለፀው ‹‹ከተጠበቀው በታች›› ተብሎ ነው፡፡ ይህም አንባቢዎችን ‹‹ውድቀት›› ከሚለው ቃል ለመከለል የተደረገ ጥረት ነበር፡፡ የአዲሱ አሰልጣኝ ብሬንዳን ሮጀርስ አጀማመር አስከፊ ነበር፡፡ ይህም የክለቡ ዝነና አሰልጣኝ ከኃላፊነት መነሳታቸው ስህተት ወይስ ለስራው ዕጩ ሆነው ቀርበው የነበሩት አንድሬ ቪያስ ቦአስ እድሉ ሊሰጣቸው ይገባ ነበር? የሚሉ እና መሰል ጥያቄዎች በደጋፊው አዕምሮ ውስጥ እንዲመላለስ አድርጎ ነበር፡፡ ቀዮቹ የውድድር ዘመኑን የጀመሩት በቀድሞው የኬኒ ዳልግሊሽ ረዳት ስቲቭ ክላርክ በሚመራው ዌስት ብሮም በአሳማኝ ሁኔታ 3-1 ተሸንፈው ነበር፡፡ ይህ አጋጣሚ በራሱ ስቲቭ ክላርክ ኃላፊነቱ ሊሰጣቸው ይገባ ነበር ወይ? የሚል ጥያቄ አስነስቷል፡፡ አጀማመሩን ይበልጥ አስከፊ ያደረገው በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ቡድኑን የተቀላቀሉት ጆአለን፣ ፋቢዮ ቦሪኒ እና ኦሳማ አሳይዲ ውጤታማ መሆን አለመቻላቸው እና ክሊንት ደምፕሴይን ለማስፈረም የተደረገው ጥረት መክሸፉ ነበር፡፡ ተጫዋቹ በይፋ የቀረበለትን ጥያቄ አለመቀበሉ የክለቡን ታማኝ ደጋፊዎች እንኳን ትንሽ ራቅ ባለ ጊዜ ቢሆንም ስሙ ከስኬት ጋር ተያይዞ ይጠቀስ በነበረው ቡድናቸው ላይ ጥርጣሬ እንዲያሳድሩ አስገድዶ ነበር፡፡ ሆኖም ውጤታማ በነበረው የጃንዋሪ የዝውውር መስኮት ክለቡ ዳንኤል ስቴሪጅ እና ፊሊፔ ኩቲንሆን ወደ ቡድኑ መቀላቀሉ መረጋጋትን አሰፈነ፡፡ የውድድር ዘመኑም ቅርፅ እየያዘ መጣ፡፡ በደረጃ ሰንጠረዡ ግርጌ ላይ ሆኖ የውድድር ዘመኑን ያጠናቅቃል ተብሎ ተፈርቶ የነበረበት ወቅት ነበር፡፡ ነገር ግን ሰባተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቀቀ፡፡ እንደ አጀማመሩ ቢሆን ከዚህም የከፋ ውጤት ይዞ ሊያጠናቅቅ ይችል የነበረበት ሰፊ ነበር፡፡ የውድድር ዘመኑ ሁለተኛ አጋማሽ ግን ጥርት ባለ መልኩም ባይሆን በቀጣዩ የውድድር ዘመን የሊቨርፑል ደጋፊዎች ምን ሊመለከቱ እንደሚችሉ የጠቆመ ነበር፡፡

2013-14 ዓለም አቀፍ ክብር
ፍፁም ተቃራኒ በሆነ መልኩ ሊቨርፑል የዘንድሮውን የውድድር ዘመን የመጀመሪያ ሶስት ጨዋታዎች በሙሉ አሸነፈ፡፡ ይህንንም ድል ያላሳከው ያለ ኮከብ ተጫዋቹ ልዊስ ሱአሬዝ እገዛ ነበር፡፡ እንደ ሲሞን ሚኞሌ እና ማማዱ ሳኮን የመሳሰሉ ተጨዋቾች በክረምቱ የዝውውር መስኮት ወደ ቡድኑ መቀላቀሉ እጅጉን ጠቅሞታል፡፡ የአያጎ አስፓስ እና ኮሎ ቱሬ ዝውውር ግን ያገኘው ድብልቅ ምላሽ ነው፡፡ ከሊቨርፑል ተጠብቆ የነበረው ደጋፊዎቹ በሹክሹክታ ‹‹ቀጣዩ የውድድር ዘመን የእኛ ነው›› ሲሉ መስማት ነበር፡፡
ከተጫዋቾቹም የተጠበቀው አራተኛ አሊያም አምስተኛ ሆነው ለማጠናቀቅ የቻሉት ያህል እንዲታገሉ ነበር፡፡ በእርግጠኝነት ያልተጠበው ነገር ዘጠን ጨዋታዎችን በተከታታይ ማሸነፉ ነበር፡፡ ቡድኑ ‹‹ጥልቀት እንደሌለው›› እየተነገረ ባለበት ሰዓት ከ34 ጨዋታዎች በኋላ በደረጃ ሰንጠረዡ አናት ላ ይቀመጣል ብሎ የረጠረጠ አለመኖሩ እውነት ነው፡፡ ሌላው ያልተጠበቀ ነገር ባርሴሎና ብሬንዳ ሮጀርስን ወደ ባርሴሎና ለማስኮብለል ሙከራ እያደረገ ነው መባሉ ነበር፡፡ ምን ይሄ ብቻ ፔፕ ጋርዲዮላ ሊቨርፑል በውድድር ዘመኑ እያሳየ ያለውን ብቃት አድቆ የአንፊልዱ ክለብ ዳግም በቻምፒዮንስ ሊግ ሲጫወት መመልከት እንደሚፈልግ ይናገራል ብሎም የጠበቀ አልነበረም፡፡

ኤቨርተን፡- ሞዬስ ተረስተዋል
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ኤቨርተን በፕሪሚየር ሊጉ ድብልቅ ውጤት አስመዝግቧል፡፡ ባለፈው የውድድር ዘመን በዴቪድ ሞዬስ የተመሩት ቶፊስ ስድስተኛ ሆነው አጠናቀቁ፡፡ ለሁለት ተከታታይ ዓመታት ከከተማ ተቀናቃኛቸው ሊቨርፑል በላይ ሆነው መጨረሳቸው ነበር፡፡ የገዘፈ ስም የነበራቸው እና እንደ ‹ጣኦት› የሚቆጠሩት ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ ሲወስኑ ዩናይትድ ሞዬስን ወደ ኦልድትራፎርድ ወሰደ፡፡ ኤቨርተንም አሰልጣኝ አልባ ሆነ፡፡ በቀጣዩ የውድድር ዘመን እንዲመሯቸውም ሮቤርቶ ማርቲኔዝን ሾሙ፡፡ ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ ስፔናዊው ከዓመት በፊትም ‹‹ንጉስ›› ዳልግሊሽን እንዲተኩ በሊቨርፑል ኃላፊነት በዕጩነት ከቀረቡ አሰልጣኞች መካከል ግንባር ቀደም ነበሩ፡፡
ማርቲኔዝ የአሰልጣንነት ዘመናቸውን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገሩት ስዋንሊ ሲቲን የታችኛው ዲቪዚዮን ሻምፒዮን በማድረግ ነበር፡፡ በዊጋን በነበራቸው ቆይታም ለሶስት ተከታታይ ዓመታት ቡድኑን ከመውረድ በመታደግ አድናቆት አትርፈዋል፡፡ በአራተኛው የውድድር ዘመን ግን ዊጋንን ወደ ታችኛው ዲቪዚዮን ከመውረድ ሊታደጉት አልቻሉም፡፡ ነገር ግን ባዶ እጁን አልሸኙትም፡፡ የማርቲኔዝ ልጆች የሮቤርቶ ማንቺንውን ማንቸስተር ሲቲ በማሸነፍ የኤፍ.ኤ ካፑን ድል ማጣጣም ቻሉ፡፡ ኤቨርተን እንዲህ ያለውን አሰልጣኝ ሲሾም ወደ ፊት እንዲያራምደው አስቦ መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡

የቻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ
ማርቲኔዝ በተጫዋቾች ዝውውር በኩል ድንቅ ስራ ሰርተዋል፡፡ በተለይ በውሰት ውል ያስፈረሟቸው ተጫዋቾች ብቃት ብዙዎችን አስገርሟል፡፡ ኤቨርተን እስካሁን ላደረገው ግስጋሴ በጊዜያዊነት ቡድኑን የተቀላቀሉት የዤራርድ ዴሌፋ፣ ጋሬት ባሪ እና ሮሜሉ ሉካኩ ሚና የጎላ ነው፡፡ ማርቲኔዝ ተጨዋቾቻቸውን የሚያስተምሩበት መንገድ ሙገሳን አስገኝቶላቸዋል፡፡ ሮስ ባርክሌይ ‹‹ቅን ሰው›› ብሎ ከገለፃቸው በኋላ ‹‹በርካታ የታክቲክ ልምምዶችን እንሰራለን፡፡ ይህ ደግሞ ለእኔ መልካም ነው፡፡ ወጣት በመሆኔ ብዙ እማራለሁ›› ሲል ለአሰልጣኙ ያለውን አክብሮት ገልጿል፡፡
ከኤቨርተን የተጠበቀው ምን ነበር? አምስተኛ አሊያም ስድስተኛ ሆነው እንዲያጠናቅቁ እና ታላላቆቹ ክለቦች በሚወዳደሩበት መድረክ የመሳተፍን ዕድል ለማግኘት መጣር ነበር፡፡ ከዚያም እንደተለመደው ባዶ እጅ መመለስ እና ከከተማ ባላንጣቸው ሊቨርፑል ጋር የበላይ ሆኖ ለመጨረስ እርባና ቢስ ፉክክር ማድረግ ተጠብቋል፡፡ ሆኖም ግምቶችን ሁሉ ውድቅ በማድረግ የቻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ የሚያስገኘውን ስፍራ ይዞ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ትግል በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ እንዳውም በአሁኑ ወቅት ቢያንስ በሂሳብ ስሌት ደረጃ የጉዲሰን ፓርኩ ቡድን ከአርሰናል በተሻለ አራተኛ ሆኖ የመጨረስ ዕድል አለው፡፡ ሌላው ቢቀር ባለፈው ክረምት ከፍተኛ ወጪ ካወጣቸው ቶተንሃም እና ከሞዬስ ዩናይትድ በላይ ሆኖ የማጠናቀቁ ነገር እርግጥ እየሆነ መጥቷል፡፡ በውድድር ዘመኑ መገባደጃ በርካታ ክለቦች ጫና ውስጥ በሚወድቁበት ሰዓት ስድስት ጨዋታዎችን ያለከልካይ ማሸነፍ ችሏል፡፡

የሜርሲ ሳይድ ደስታ እና ጥርጣሬ
ሁለቱ የመርሲ ሳይድ ክለቦች ምርጥ እግርኳስ ይጫወታሉ፡፡ የሚፈልጉትን ውጤት ማስመዝገባቸው ብቻ ሳይሆን ኳስን የሚጫወቱበት መንገድ በራሱ አስደናቂ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በፕሪሚየር ሊጉ ሲያጠቃ እጅግ የሚያስፈራው ቡድን ሊቨርፑል ነው፡፡ በመልሶ ማጥቃት ቡድኖችን ከጥቅም ውጪ የሚያደርግበት መንገድ ለተመልካች አዝናኝ ነው፡፡ ኤቨርተንም ቢሆን መልካም እግርኳስ ይጫወታል፡፡ በተለይ በክንፍ በኩል ማጥቃት አሁንም የኤቨርተን መታወቂያው ነው፡፡ ስቲቭ ፒናር እና ሌይተን ቤይንስ በግራ መስመር የሚሰነዝሩት ጥቃት በሞዬስ ዘመንም የነበረ ነው፡፡
ሺመስ ኮልማን እና ኬቪን ሚራላስ በቀኝ መስመር የፈጠሩት የማጥቃት አማራጭ ግን የማርቲኔዝ ውጤት ነው፡፡ ባሪ እና ጀምስ ማካሪቲ የመሀል ሜዳውን ለመቆጣጠር በሚያደርጉት ያላሰለሰ ጥረት አማካይ ክፍሉ የበለጠ የተረጋጋ ሆኗል፡፡ ሁኔታውን ትኩረት ግቢ የሚያደርገው ኤቨርተን የከተማ ተቀናቃኙ ሊቨርፑል ለዋንጫ የሚያደርገውን ጉዞ ማገዙ ነው፡፡ ኤቨርተን የሚገኘው ቀሪዎቹን ጨዋታ በሙሉ የሚያሸንፍ ከሆነ ቻምፒዮንስ ሊግ መሳተፍ የሚያስችለው ደረጃ ማግኘት በሚችልበት ሁኔታ ነው፡፡ በመሆኑም ሊቨርፑል በማሸነፉ የሚገፉበት ከሆነ እና ኤቨርተን በሜዳው ከሲቲ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ማሸነፍ ከቻለ የከተማ ተቀናቃኙ ሻምፒዮን እንዲሆን የበኩሉን አስተዋፅኦ አበረከተ ማለት ነው፡፡ አንዳንድ የኤቨርተን ደጋፊዎች ግን መራራ ባላንጣቸው ሊቨርፑል ለ19ኛ ጊዜ የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሲሆን ከመመልከት ይልቅ የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ ቢቀርባቸው እንደሚመርጡ በመናገር ላይ ናቸው፡፡
ሆኖም እንደ ስልቨ ደስቲን እና ሮስ ባርክሌይን የመሳሰሉ ተጨዋቾች የቻምፒዮንስ ሊግ ምሽቶች ወደ ጉዲሰን ፓርክ ቢመጡ ደስታቸው ወደር እንደማይኖረው በመናገር ላይ ናቸው፡፡

ገንዘብ ተሸንፏል
ሊቨርፑል እና ኤቨርተን በብሪታኒያውያን ተጨዋቾች ዙሪያ ቡድናቸውን መገንባታቸው ድንቅ ሀሳብ እንደሆነ በፌዝ መልክ በተደጋጋሚ ተነግሯቸዋል፡፡ አባባሉ የመነጨው በክለቦች የሚያድጉ ተጨዋቾች ከሌሎች ሊጎች ከሚመጡ ተጨዋቾች በብቃት ያነሱ ናቸው ከሚል እሳቤ ነው፡፡ ምፀታዊው ነገር ግን ሮይ ሆጅሰን ወደ ብራዚል ይዘውት በሚሄዱት ስኳድ ውስጥ ቢያንስ ስምንት ተጨዋቾችን ከሜርሲ ሳይድ ሊመርጡ የሚችሉ መሆኑ ነው፡፡ ስቲቨን ዤራርድ፣ ዳንኤል ስቱሪጅ፣ ራሄም ስቴርሊንግ፣ ጆርዳን ሄንደርሰን፣ ግሌን ጆንሰን፣ ሌይተን ቢይንስ፣ ፊል ጃግዬልካ እና ሮስ ባርክሌይ ወደ ደቡብ አሜሪካዊ ሃገር የመጓዝ ዕድላቸው የሰፋ ነው፡፡ ሊቨርፑል ዳግም እንደሚያንሰራራ አሊያም ወደ ክብሩ ሰገነት እንደማይመለስ ተገንብዮ ነበር፡፡ ኤቨርተንም ቢሆን የውጭ ባለሀብት የክለቡን ባለቤት ቢል ኬንራይትን እስካልተካ ድረስ ምንም የተለየ ነገር እንደማይፈጥር ተደምድሟል፡፡ በአሁኑ ወቅት ግን ሁለቱ የሊቨርፑል ክለቦች በእግርኳስ ከገንዘብ ይልቅ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባው ቴክኒክ፣ ክህሎት እና ጥሩ አሰለጣጠን ለመሆናቸው ጥሩ ማሳያ ሆነዋል፡፡ በቅርቡ ሊቨርፑልን የተቀላቀሉት ተጨዋቾች በሙሉ ለሊቨርፑል መነቃቃት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዳበረከቱ አይካድም፡፡ ሱአሬዝን ማቆየት ከፍተኛ ወጪ እንደጠየቀም አይታበልም፡፡ ሲጀመር እርሱን ማግኘት በራሱ ፈተና ነበር፡፡ ነገር ግን ሁሉም ነገር የተቀባባ አልነበረም፡፡ ሊቨርፑል በፕሪምየር ሊጉ አሁን ያለበትን ደረጃ የተቆናጠጠው ባለፈው ዓመት ባፈሰሰው መዋዕለ ንዋይ ምክንያት አይደለም፡፡ ከሰባተኛ ወደ አንደኛ ደረጃ መምጣት የማይታሰብ ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ አድናቆት ሊቸረው የሚገባ ነው፡፡ ኤቨርተንም ቢሆን ይህን ያሳካው በገንዘብ እርዳታ ብቻ አይደለም፡፡ አሰልጣኛቸው አዲስ ታክቲክ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ በሜዳ ውስጥ እና ከሜዳ ውጪም ብልህ ነበሩ፡፡ ይህም ልፋታቸውም አንፀባራቂ የውድድር ዘመን አስገኘላቸው፡፡ ከነበሩበት ተራነትም ወደ ከዋክብትነት ተለወጠ፡፡
ሊቨርፑል እና ኤቨርተን የዘንድሮው ፕሪሚየር ሊግ ክስተቶች ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ቀጣዩ ዓመት ለከተማዋ በጣም አስደሳች መሆኑ አይቀሬ ነው፡፡ የቻምፒየንስ ሊግ ምሽቶች ወደ ከተማዋ የሚመለሱ ከሆነ በርካታ ጎብኚዎች መጉረፋቸው ስለማይቀር የከተማዋ ገቢም እመርታን ያሳያል፡፡ ከእግርኳሷዊ አንፃር ብቻ ከተመለከትነው ሁሉም ተገንታኞች፣ አሰልጣኞች እና የሌሎች ክለብ ደጋፊዎች ቆም ብለው እነዚህን ሁለት ክለቦች ለማየት ይገደዳሉ፡፡ አምነው ባይቀበሉም እንኳን በእነዚህ ሁለት ቡድኖች ትንሣኤ መማረካቸው እውን ነው፡፡

የወያኔን መንግስት በመቃወም በኖርዌ ኦስሎ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ

$
0
0

nor34በኖርዌ ኦስሎ ሜይ 8 ቀን 2014 (ሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም ) የወያኔ መንግስት በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ:ያደረሰውን ግድያ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ :

በኦሮሚያ ክልል በከፍተኛ የትምህርት ተቋማትበሚማሩ የኦሮሞ ተማሪዎች ላይ የወያኔ መንግስት ሀይሎች በወሰዱት እርምጃ ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የሰው ህይወት መቀጠፉና ብዙዎችም ለአካል ጉዳት መዳረጋቸው ይታወቃል::

ይህንንም ተከትሎ በኖርዌ ኦስሎ ከተማ በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አዘጋጅነት ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ የተደረገ ሲሆን በሰላማዊ ሰልፉ ላይ በመቶዎቹ የሚቆጠሩ በኦስሎና በተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች የድጋፍ ድርጅቱ ባደረገላቸው ጥሪ መሰረት ሰልፉ በተጀመረበት ቦታ በመገኛት በግፍ ለሞቱት የኦሮሞ ተማሪዎች የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት ካደረጉ በኋላ ዘረኛውና አንባገነኑ የወያኔ መንግስት በኦሮሞ ወጣት ተማሪዎች ላይ ያደረሰውን የአካል ጉዳትና ግድያ በመቃወም ድምጻቸውን አሰምታዋል ::

ሰላማዊ ሰልፉ በኖርዌ የሰአት አቆጣጠር ከቀኑ 15:00 ጀምሮ እስከ 17:30 የተደረገ ሲሆን በሰላማዊ ሰልፉላይ የተገኙ ኢትዮጵያኖች በሰላማዊ መንገድ ጥያቄቸውን ሲጠይቁ በነበሩ የኦሮሞ ተማሪዎች ላይ ጥይትን በማዝነብ ኢሰብሃዊ ድርጊት የፈጸመውንና ቡዙዎችን የገደለውን የወያኔን መንግስት የሚያወግዙ የተለያዩ መፈክሮችን በማያዝ እና በማሰማት ተቃውሞቸውን በሀይል ገጸዋል:: በሰልፉ ላይ ሰልፈኞቹ ያሰሟቸው ከነበሩት መፈክሮች መካከል የወያኔ መንግስት ገዳይ መንግስት ነው፣ የኦሮሞ ተማሪዎችን በጅምላ መግደል ይቁም፣ በኢትዮጵያ በጅምላ ስለተገደሉት የኦሮሞ ተማሪዎች አዝነናል፣የታሰሩ የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ፣የሚሉ ይገኙበታል::

 

nor 35ሰልፈኞቹ በቀጥታም ወደ ኖርይጅዋያን ፓርላማ ጽህፈት ቤት በመሄድ ለኖርዌ መንግስት ጉዳዩን በግልጽ ያሳ ወቁ ሲሆን ኖርዌ ከወያኔ መንግስት ጋር ያላትን ግንኙነት እንድትመረም ጠይቀዋል:: በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ፣ ከጋራ መድረክ፣ ከስደተኞች ማህበር፣ከሸንጎ፣ከኢትዮጵያ ማህበር ኖርዌ የተገኙ መሪዎችና ተወካዪች የወያኔን ግፍ በመቃወም ንግግር አድርገዋል::በመጨረሻም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ ሊቀመንበር አቶ ዮሀንስ አለሙ የድርጅታቸውን አቋም ሲገልጹ ድርጅታቸው በድርጊቱ በጣም እንዳዘነና በጥቃቱ ሰለባ ለሆኑና ለሞቱ ዜጎች ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን በመመኘት የታሰሩ ወጣት የኦሮሞ ተማሪዎች በአስቸኮይ እንዲፈቱ፣ የዚህም ድርጊት ፈጻሚ አንባገነኖች በአስቸኮይ ለፍርድ እንዲቀርቡ በመጠየቅ የድርጅቱን የአቋም መልክት ለኖሮዊጅያን ምክር ቤት ተወካይ ያስረከቡ ሲሆን የምክር ቤቱም ተወካይ ንግግር አድርገው ሰላማዊ ሰልፉ በተያዘለት ሰአት ተጠናቋል::

 

ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ

 

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

 

 

 

 

 

የአበበ ገላው “ጩኸት”አንደምታ (ዳጉ ኢትዮጵያ)

$
0
0

ዳጉ ኢትዮጵያ (dagu4ethiopia@gmail.com)

620አንድ የማህበራዊ ድረ-ገጽ ወዳጄ “በአበበ ገላው የሰሞኑ ድርጊት ምን አስደሰተህ?” ሲል ግራ በመጋባት ጠየቀኝ፡፡ የወዳጄ ጥያቄ የአበበ ገላው በፕሬዚደንት ኦባማ ፊት የኢትዮጵያውያንን የነፃነት ጩኸት ማስተጋባት በኔ በኢትዮጵያ ምድር የምኖር ዜጋ ላይ ስለሚኖረው አንደምታ በጥልቅ እንዳስብ አደረገኝ፡፡

ዜጎች ሐሳባቸውን በነጻነት መግለጽ በማይችሉባት ሐገር፤ ይልቁንም “ለዚህ ሥርዓት ጥሩ አመለካከት የለህም፣ የወጣት ሊግ፣ የሴቶች ፎረም፣ የነዋሪዎች ፎረም ወዘተ በተሰኙ የስርዓቱ አደረጃጀቶች አልተሳተፍክም” በሚል – መገለል፤ ባስ ሲልም መዋከብና ከስራ መፈናቀል በሚደርስበት ሐገር የማስበውን የሚተነፍስልኝ፣ አንደበት የሚሆንልኝ ሳገኝ ብደሰት፣ ባሞግሰው – ጀግና ብለው ምን ይገርማል? የህዝቡን ይሁንታ አግኝቼ ተመርጫለሁ፣ ኮንትራት ተሰጥቶኛል ወዘተ የሚል ማመካኛ እየደረደረ በምከፍለው ግብር የሚተዳደሩ የህዝብ ንብረት የሆኑ ሚዲያዎችን ወደራሱ የግል ንብረትነት አዛውሮ ጠዋት ማታ ሳልጠግብ – ጠግበሃል፣ በሥራ አጥነት እየተንከራተትኩ – ሥራ በሽ በሽ አድርጌልሃለሁ፣ የኑሮ ውድነቱ አጉብጦኝ – ኑሮህ ተሻሽሏል እያለ የራሱን ሹማምንት ምቾት የኔ እንደሆነ አድርጎ ለኔው የሚለፍፍ ስርዓት ባለበት ሐገር የነጻነት ጥማቴን የሚናገርልኝን አበበን ባወድሰው የሚያስገርመው ምኑ ነው?

በአምቦ፣ ሐሮማያ፣ አፋር፣ ምዕራብ ወለጋ፣ ተምቤን፣ ጎንደር ወዘተ በወንድም እሕቶቼ፣ በእናት አባቶቼ ላይ የሚደርሰውን አፈና፣ ግርፋት፣ ከመኖሪያ ማፈናቀል፣ ግድያ፣ አላግባብ ከስራ ማባረር ወዘተ ሳወግዝ “የ… ከተማ ነዋሪዎች መንግስት የወሰደውን እርምጃ አደነቁ… ከግድያው የተረፉትም አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድባቸው ጠየቁ” እየተባለ በስርአቱ የፕሮፖጋንዳ አንደበቶች ጩኸቴን ስቀማ – ያልኩት ቀርቶ ለመንግስት ጆሮ የሚጥመው በኔ ስም ሲነገር – አበበ ትክክለኛውን ጩኸቴን ሲጮህልኝ እልል ብል፣ ትክክለኛ ብሶቴን ለአደባባይ ሲያበቃልኝ አበጀህ ብለው ተሳሳትክ የሚለኝ ማነው?

በሐገር ውስጥ በመሆን ስርዓቱ ያሰፈነውን የፍርሐት ቆፈን ወግድ ብለው በብዕራቸው ብሶቴን የተነፈሱልኝን፣ ጩኸቴን የጮሁልኝን ተቃዋሚዎች፣ በጋዜጠኝነት ሙያቸው አገዛዙ ያመጣብኝን የመረጃ ረሐብ ሊያስታግሱልኝ የሞከሩ ጋዜጠኞችንና ጦማሪያንን ሰብስቦ በፈጠራ ክስ በእስር ሲያጉራቸው አሰፈንኩት ብሎ ያሰበውን የህዝብ ድምጽ እርጭታ በነጎድጓዳማ ድምፁ የሰበረልኝን – ስርዓቱ ለሚዘጋው እያንዳንዱ በር በአንጻሩ በትግል የሚከፈት ሌላ በር እንደሚኖር በተግባር ያረጋገጠልኝን አበበን አበጀህ የኔ አንደበት ብለው ወዴት ላይ ነው ጥፋቴ?

“የዋህ ነህ – የአበበ ገላው ድምጹን ማሰማት ስርዓቱን አያፈርሰውም፣ ኦባማ በስርዓቱ ላይ ማዕቀብ እንዲጥል፣ በአደባባይ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰውን በደል እንዲያወግዝ አያደርገውም” ይሉኛል፡፡ እኔስ እሱን መች ጠበቅኩና? ለተበዳይ በደሉ መሰማቱ በራሱ የድሉ መጀመሪያ መሆኑን አታውቁም? ለታፈነ ሰው ጩኸቱ ለአደባባይ መብቃቱ፣ በደሉ ለጆሮ መድረሱ በራሱ ስኬት ነው፡፡ እንጂማ ጀርባዬ ላይ ሆኖ የሚያጎብጠኝን፣ እንደ እንስሳ ስለ ሆዴ እንጂ ስለ ነጻነቴ እንዳልጠይቅ የሚያስፈራራኝን፣ ስራ፣ የመኖሪያ ቤት ወዘተ በጥረቴ ሳይሆን ለስርዓቱ ባጎበደድኩት መጠን የማገኘው ድርጎ ያደረገብኝን ስርዓት ወግድልኝ ብሎ የማሽቀንጠሩ ኃላፊነት የኦባማ ሳይሆን የኔ መሆኑን መቼ አጣሁት? ገዢዎቼ የወንበር ስስት፣ የስልጣን ስጋት ስላለባቸው የአቤን ድርጊት ከወንበራቸው ከመነቅነቅ አንጻር ሊመዝኑት ይፈልጋሉ፡፡ የኔ መስፈሪያ ሌላ ነው፡፡ የማይወክለኝን ከወንበሩ የመነቅነቁ፣ ከምርጫ ኮሮጆ በመጣ የዜጎች ይሁንታ ሳይሆን ከሩስያ በመጣ የኤኬ 47 ጠመንጃ ጉልበት መንግስትነትን የያዘውን ስርአት የማንኮታኮቱ የቤት ሥራማ የኦባማ አስተዳደር ሳይሆን የኛ የኢትዮጵያውያን የመሆኑን ሐቅ መቼ ሳትኩት?

ደግሞስ እውነትን በሐይል ለስልጣን መናገር ያለውን ጉልበት መቼ አጣችሁት? ይኸው አበበ አይደል እንዴ በሐገር ውስጥ በጠመንጃና በእስር ቤት ሐይል፣ በውጪ ሐገር በብልጣ ብልጥነት ሸፋፍነው ይዘውት የነበሩትን የአምባገነንነት ማንነት በአለም አደባባይ እርቃኑን አስቀርቶ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር ለክውታ (ምናልባትም ለህልፈት)፣ የስርአቱን ቲፎዞዎችም ለከፍተኛ ብስጭት የዳረገው? ትግሉ ፈርጀ ብዙ መሆኑን አትርሱ እንጂ፡፡ የቀድሞው መሪ ድምጻችን ይከበር ብለው ወረቀት ይዘው አደባባይ የወጡ ወንድሞቻችንን ግንባር በአልሞ ተኳሾቻቸው አስነድለው መቼ ዝም አሉ? “ባንክ ሊዘርፉ ሲሉ ተገደሉ” ብለው በወጣቶቹ ወላጆች ላይ የስነ ልቦና ጦርነት አልከፈቱም? ይህን ግፍ ያዩ ብዙዎች በኢትዮጵያ ሰማይ የእውነትና የፍትሕ ፀሐይ መቼም አትወጣም ብለው ተስፋ እንዲቆርጡ አልደረጉም? ስለዚህ የአበበ ድርጊትም አፋኞቻችንን – “እውነት ታፍና መቼም አትቀርም፤ ጠመንጃም የእውነትን ወሊድ ያዘገየው ይሆናል እንጂ እስከወዲያኛው አያስቀረውም” የሚለውን ሃቅ በአእምሯቸው እንዲያቃጭል ማድረጉ በራሱ ድል አይደለም? ይልቁንም ክስተቱ የተፈፀመው የስርአቱ ጥቅመኞች ቀድሞ በአካል፣ ሞተውም በ”ራዕይ” የሚመሯቸውን ግለሰብ ልደት ለማክበር ተፍ ተፍ ሲሉበት በነበረው ወቅት መሆኑ በስርአቱ ደጋፊዎች ላይ የፈጠረውን የስነ ልቦና ጉዳት እስኪ ወደ ማህበራዊ ድረ-ገፆች ጎራ በሉና ታዘቡ!

“አበበ አንድ ግለሰብ ነው… ጩኸቱም ምንም ለውጥ አያመጣም” ይላሉ፡፡ እንዴ… የነፃነት መንፈስ እኮ ሁሌም ሲጀመር በአንድ ወይም በጥቂት ሰዎች ነው፡፡ ደግነቱ ግን ቶሎ ይዛመታል፡፡ ውቂያኖስ ሳይገታው፣ ፖለቲካዊ ድንበሮች ሳያስቆሙት፣ የመረጃ አፈና ሳያግደው ወደሺዎች ከዚያም ወደ ሚሊዮኖች ይጋባል፡፡ ምርጫ 1997ን ማስታወስ ይቻላል፡፡ ጥቂቶች የነፃነት መንፈስን ከታሰረበት ፈተው ለቀቁት፡፡ በወራት ጊዜ ውስጥ ከገጠር እስከ ከተማ – ከድሐ ጎጆ እስከ ቤተ መንግስት ተቆጣጠረው፡፡ ዛሬም በአበበ ገላው የተለኮሰው የነጻነት ችቦ የነጻነት እጦት ብርድ ሆኖ ያንዘፈዘፈንን በሙቀቱ ሲያፍታታን፤ የአምባገነንነት ትኩሳት ጭንቅላታቸው ላይ የወጣውን ገዢዎቻችንን ነበልባል ሆኖ ሲፈጃቸው መመልከታችን አይቀሬ ነው፡፡

እናም … እናም… እናም… በወንድሜ አበበ ገላው ሥራ ደስ ተሰኝቻለሁ – ተነቃቅቻለሁ – ተስፋንም ሰንቄያለሁ፡፡ ነገ ይህ የነፃነት ስሜት በአእላፋት ላይ ተጋብቶ ገዢዎቻችንን በየሔዱበት ሲያስጨንቅ፣ አንገት ሲያስደፋ፣ ሲያብረከርክና ሲያፍረከርክ አሻግሬ እያየሁ…

 

አስደንጋጭ የእሳት አደጋ

$
0
0

ምንሊክ ሳልሳዊ
213ከጎተራ ማሳለጫ ወደ ቄራ በጓዝ ላይ የነበረ ነዳጅ የጫነ የፈሳሽ ማመላለሻ መኪና ከነተሳቢውና ተሳፋሪ ጭኖ ከቄራ በኩል ይጓዝ የነበረ ሚኒባስ ታክሲ ሞሐ ለስላሳ መጠጦች ፋብሪካ(ፔፕሲ) ፊት ለፊት ራሳቸውን ከመጋጨት ለማትረፍ ባደረጉት ጥረት ተሳቢው ታክሲው ላይ ተገልብጦ በደረሰ ከፍተነኛ የእሳት አደጋ ሰዎች ተቃጠሉ።

በአሁኑ ሰዓት የተቃጠሉ አስክሬኖች እየተለቀመ ነው።ተጎጂዎች ወደ ሆስፒታል እየተወሰዱ ነው።አደጋው ከደረሰ አንድ ሰዓት ሆኖታል። የዐይን እማኞች እንደተናገሩት ተሳቢው ታክሲው ላይ በወደቀበት ቅጽበት ሚኒባስ ውስጥ ያሉትን ሰዎች ለማትረፍ ርብርብር የተደረገ ቢሆንም ተሳቢው ውስጥ የነበረው ነዳጅ በመፍሰሱ በድንገት ከፍተኛ እሳት ተነስቷል።በዚህን ጊዜ ሁሉም ራሱን ለማዳን መራወጥ ጀመረ።

እንደምንም ከሚኒባሱ ውስጥ የወጡ ሰዎች እሳት እየነደደባቸው ራሳቸውን ለማትረፍ ሲሞክሩ ታይተዋል። አደጋውን ተከትሎም በአካባቢው ወዲያው የደረሱ መኪኖች ተጋጭተዋል። አካባቢው በከፍተኛ ጭስ ታፍኖ ነበር። (ምንሊክ ሳልሳዊ)

214


Video: አንድነት ፓርቲ በአዲስ አበባ ሚያዝያ 26 ያካሔደው ሰላማዊ ሰልፍ ክፍል 3

የእስረኛው ‹‹ጋዜጠኝነት›› ሌላ ፈተና –በጽዮን ግርማ

$
0
0

tsiongir@gmail.com
(ፋክት መጽሔት ላይ የታተመ)

የ2012ቱ የአሜሪካ ፕሬዝዳታዊ ምርጫ ከመከናወኑ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ስለምርጫውና የአሜሪካ የጋዜጠኝነት ኹናቴ እንዲወያዩ በአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት አዳራሽ ከተጋበዙና ከሰማንያ የዓለም አገሮች ከተውጣጡ አንድ መቶ ሠላሣ ተሳታፊ ጋዜጠኞች መካከል አንዷ ነበርኹ፡፡ ልምዳቸውን እንዲያካፍሉ ከተጋበዙ የአሜሪካ አንጋፋ ጋዜጠኞች መካከል ታዋቂው የዋሽንግተን ፖስት ጋዜጠኛ ቦብ ውድዋርድ አንዱ ነበር፡፡
zone 9999
ቦብ በስቴት ዲፓርትመንት ሕንፃ አዳራሽ ከሌላ አገር ለመጡ ጋዜጠኞች፤ በምርመራ ጋዜጠኝነት ሥር አጨቃጫቂና አንገብጋቢ ጉዳዮችን ሲዘግቡ በአሜሪካ መንግሥት የሚያጋጥማቸውን ፈተና እየዘረዘረ፣ ዓለም የሚደነቅበትን የአገሩን የመናገርና የመጻፍ ነፃነትና ‹ዴሞክራሲያዊ› የምርጫ ሂደት የፕሬዝዳንት ኦባማን ስም ሳይቀር በስም እየጠቀሰ በሒስ ሲሰልቀው ከፍርሃት ነፃ በኾነ ከፍተኛ የራስ መተማመን መንፈስ ተሞልቶ ነበር፡፡

በወቅቱ የስቴት ዲፓርትመንት ከፍተኛ ባለሥልጣናት “The price of politics” የሚለውን ባለሠላሳ ዶላር መጽሐፉን ፈርሞ በቦታው ለተገኘነው ጋዜጠኞች በስጦታ እንዳበረከተልን ተናግረው ሲያስጨበጭቡን ቦብ በስጨት ብሎ በማቋረጥ፣ ‹‹መጽሐፌን ለማንም በነፃ አልሰጠኹም፤ ስቴት ዲፓርትመንቱ ነው ገዝቶ የሰጣችኹ›› በማለት ሲያሸማቅቃቸው በፈገግታ ነበር ያለፉት፡፡ እንግዲህ የዓለም ጋዜጠኞች በተሰበሰቡበት በኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አዳራሽ አንድ አንጋፋ ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ መሪውንና ሥርዓቱን ሲተች በምናብ ማየት ነው!!

ውይይቱ ሲያበቃም ለጋዜጠኛው ክብር ሲባል በየቡድናችን እየተጠራን ባለበት ሔደን የማስታወሻ ፎቶ እንድንነሣ ስንጋበዝ ባለሥልጣናቱ ለጋዜጠኛው ያላቸው ክብር በግልጽ ይታይ ነበር፡፡ ሞጋች ጋዜጠኞች ከሚሰደዱበት፣ ከሚታሰሩበት አልያም በፍራቻ ሥራ ከሚያቆሙበት ወይም ከፍ ዝቅ ተደርገው እየተመናጨቁ መረጃ ከሚከለከሉበት፣ ከፖለቲካዊና ገዢዎችን ከሚነካ ዘገባ ይልቅ ወደ ማኅበራዊና መዝናኛ ጉዳዮች እንዲያተኩሩ በእጅ አዙር ከሚገደድበት አገር ለሔደች ለእንደኔ ዓይነቷ ጋዜጠኛ የስቴት ዲፓርትመንቱ ባለሥልጣናት ለአንጋፋው የዋሽንግትን ፖስት ጋዜጠኛ ቦብ ውድዋርድ የቸሩት አክብሮት ቢያስደምመኝም የጋዜጠኝነት ሞያ እንዲያ ተከብሮ የሚያስከብር መኾኑን አላጣኹትም ነበር፡፡

ጋዜጠኝነት እንደሞያ እጅግ የተከበረ ነው፡፡ ጋዜጠኝነት በአቀራረቡ ባለብዙ መልክ ቢኾንም የብልሹ አስተዳደርና አሠራር ችግሮችን ነቅሶ ለማውጣት፣ ከሕዝብ የተሰወሩ በደሎችን ለማጋለጥ፣ ከሕግና ሥርዓት ውጭ የኾኑ ባለሥልጣናትን በዐደባባይ ለመተቸትና ለማጋለጥ፣ ለሕዝብ ዋስ ጠበቃ በመኾን የሚያገለግል በተለምዶ አጠራር ‹አራተኛ መንግሥት› ነው፡፡

ከሚዛናዊነት፣ እውነትና ፍትሕ ጋር የሚሠራ “ሞያዊ ጋዜጠኛነት” (Professional journalism) ለዴሞክራሲዊ አስተሳሰብና ተግባር ዋናው አንቀሳቃሽ ሞተር ነው፡፡ ከፍርሃትና ስጋት የተጠበቀ፣ ከተገዢነትና አገልጋይነት የጸዳ ጋዜጠኝነት የሚወደድ ሞያ ነው፡፡ ሞያዊ ጋዜጠኝነት አገልጋይነቱ በቀጥታ ለሕዝብ ስለኾነ ኹሌም ለውጥ በማምጣት ሒደት ውስጥ ዋና ተሳታፊ ነው፡፡ ሞያው ነጻ በወጣባቸው አገሮችም ልክ እንደ ቦብ ውድዋርድ ተከብረው የሚያስከብሩ ጋዜጠኞች ይፈጠራሉ፡፡

በጋዜጠኝነት ሞያ የኢትዮጵያን ነባራዊ ኹኔታ ብናይ፤በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት በአገሪቱ ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እንደተከበረ በተለያየ መንገድ ያውጃል፡፡ መልሶ ደግሞ ይህን መብት ገደብ አልባ በኾኑ የተለያዩ መንገዶች ሲያፍነውና ሲጨቁነው ይታያል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው አሠራር በተለይ የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያው ነጻነት ሙሉ በሙሉ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ወድቋል፡፡ ለግል የተፈቀዱት ከአንድ እጅ ጣቶች የማያልፉ ሬዲዮ ጣቢያዎችም ቢኾኑ ነፃነታቸው የተረጋገጠው በመዝናኛ ዝግጅቶችና በጥቂት የማኅበራዊ ጉዳይ ዘገባዎች ብቻ ነው፡፡ የኅትመት ብዙኃን መገናኛን በሚመለከትም በርካታ ጋዜጣና መጽሔቶች በየወቅቱ ቢታዩም በተለያየ ምክንያት ስለሚቋረጡ በገበያው ረዘም ላለ ጊዜ የሚቆዩት ጥቂቶቹ ናቸው፡፡

እስረኛው ‹‹ጋዜጠኝነት›› በኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ውስጥ የጋዜጠኝነት ሞያ በራሱ ነፃ ያልወጣ እስረኛ ነው፡፡ በገዢው ግንባር ቁጥጥር ሥር የሚገኙ ብዙኃን መገናኛዎች በመንግሥት ጥቅም ልክ የሚሠሩና ድጋፍ ብቻ የሚሰጡበት ‹‹ጋዜጠኝነት›› ነው፡፡ ከግንባሩ አስተሳሰብና አሠራር የሚነጨው ይኸው የሞያው እስረኝነት ላለፉት ኻያ ሦስት ዓመታት ሲሠራበት የቆየ ነውና አያጠያይቅም፡፡ በግለሰብ ባለቤትነት በሚመሩ የኅትመት ብዙኃን መገናኛዎችና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተጀመረው የዲጂታል ሚዲያ ላይ ተግባራዊ የሚደረገው ጋዜጠኝነትም በበርካታ ተጽዕኖች ሥር የወደቀ ጋዜጠኝነት ነው፡፡ በተለይ ከምርጫ 97 ጀምሮ ጠንካራ ክንድ ተጭኖ ይዞታል፡፡

የመንግሥት ባለሥልጣናት በሚሰጧቸው መግለጫዎች ጋዜጠኛውን የሚያንቋሽሹ ቃላትን በመጠቀም በግል ብዙኃን መገናኛ ላይ የሚሠሩ ጋዜጠኞች አገሪቷን ወደተሳሳተ መንገድ የሚመሩ አጥፊዎች አድርጎ መሣል የተለመደ ነው፡፡ የወንጀል ሕጉ ውስጥ ጋዜጠኛን በሚመለከት የተካተቱት አንቀጾች፣ የመገናኛ ብዙኃን ዐዋጅና የፀረ ሽብር ዐዋጁ ጋዜጠኝነትን አስረው የሚያስቀምጡ መቆጣጠሪያ መሣሪያዎች ናቸው፡፡

በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ባሉ የኤሌክትሮኒክስና የኅትመት ሚዲያ አማካይነት በየዕለቱ በጋዜጠኞች ላይ የወቀሳ ናዳ በማውረድ ሞያው ነፃነቱን እንዲያጣ ያደርጉታል፡፡ በመንግሥት ብዙኃን መገናኛዎች ውስጥ ያሉ ጋዜጠኞች የነፃነታቸው ጉዳይ ሳያሳስባቸው በግል የሚሠሩ ጋዜጠኞችን የሚያንኳስስ ተደጋጋሚ ዘገባ ማቅረብን ለአለቆቻቸው እንደ እጅ መንሻ ይጠቀሙበታል፡፡

በኾነው ባልኾነው ጋዜጠኞችን እየጠሩ ማስፈራራት፣ መክሠሥና ማሰር ሞያውን የበለጠ እንዲኮሰምን ያደርገዋል፡፡ መተቸትን አብዝቶ የሚጠላው መንግሥት በአገዛዙና በሥርዓቱ ላይ ጠንካራ ትችት የሚያቀርቡ ጋዜጠኞች ሲወጡ ‹‹ከጀርባቸው እገሌ የሚባል አሸባሪ ድርጅት አለ›› ወይም ደግሞ ‹‹እገሌ ከሚባል አገሪቱን ለማተራመስ ከሚሠራ አካል ላይ ገንዘብ ተቀብለዋል›› በሚል ፈርጆ ሞያውን አስሮ ያስቀምጠዋል፡፡ ለመረጃ ነፃነትና ለጋዜጠኝነት ሞያ ድጋፍ በመስጠት ከማሳደግ ይልቅ ገና ብቅ ሳይል አናት አናቱን በማለት እዛው ያስቀረዋል፡፡

በሌላ በኩል የመንግሥት ተፎካካሪ የኾኑ የተቃዋሚ ፓርቲ ድርጅቶችም ምንም እንኳን ራሳቸው በበርካታ የመንግሥት ጫና ሥር የሚገኙ ቢኾኑም ትችት የሚያቀርብባቸውን ጋዜጠኛ ላይ ተጽዕኖ ለማሳረፍ አይሰንፉም፡፡ እነርሱን የሚተች ጋዜጠኛ ቅጥያ ይለጠፍበትና የመንግሥት ደጋፊ ተደርጎ ይፈረጃል፡፡ በተለይ እርስ በርስ ስምምነት በሚያጡበት ጊዜ ኹሉም ጋዜጠኛውን ወደ ራሳቸው ጎራ ለመጎተት ይሞክራሉ፡፡ እንቢተኝነትን ያሳየ ወይም ደግሞ ድርጊቱን የተቃወመ ጋዜጠኛ ስሙ ከአንዱ ድርጅት ወይም ግለሰብ ጋር ተዳብሎ ሞያዊ ክብሩን ይገፈፋል፡፡

ጥቂት በማይባሉ አንባብያን ዘንድ ደግሞ ጋዜጠኛው ያቀረበውን መረጃ ትክክለኛነት በሒደት መዝኖ እውነቱን ከማወቅ ይልቅ ፍረጃውን ተከትሎ አብሮ የመዝመም ዝንባሌ ይታያል፡፡ በፍረጃ ፍዳውን ባየ ጋዜጠኛ ላይ ውግዘት ይጨምርበታል፡፡ የማንበብ ፍላጎቱም የሚዘልቀውም የኾነውን የተፈጠረውን ሳይኾን እርሱ እንዲኾን የሚፈልገውን ብቻ ነው፡፡ ጉዳያቸው ብዙኃን መገናኛ ላይ ለመቅረብ ብቁ የኾነም ያልኾነም ግለሰቦች፣ የንግድ ተቋማት፣ አርቲስቶችና ሌሎች አካላትም የሚጻፉት ነገሮች ኹሉ በእነርሱ ፍላጎት ልክ እንዲኾን ይወተውታሉ፡፡ ከፍላጎታቸው ውጭ ከተጻፈና ከተዘገበ ደግሞ ከቻሉ መክሰስ ካልኾነ ደግሞ ጋዜጠኛውን ማንቋሸሽና ጠልፎ ለመጣል ሙከራ ያደርጋሉ፡፡ ምንም እንኳን ሕትመቱ ከመውጣቱ በፊት ቅድመ ምርመራ (censorship) ባይኖርም ከማቀድና ከመጻፍ በፊት ጋዜጠኛው በግሉ ፤የራስ በራስ ምርመራ (self censorship) በማድረግ የሞያውን ነጻነት አሳልፎ ይሰጣል፡፡

ሞያው ነጻነት ባጣ ቁጥር ዕድገቱ እየኮሰመነ ስለሚሄድ የሞያው ተፈላጊነት ይቀንሳል፡፡ በዕውቀትና በክህሎት ብቁ የኾኑ አብዛኞቹ ባለሞዎች ሥራቸውን ይቀይራሉ አሊያም አገር ጥለው ይሰደዳሉ፡፡ ዕለት ከዕለት ሞያውን የሚቀላቀሉት ባለሞያዎችም ብቃት አነስተኛ ስለኾነ ቁንጽል የሆኑ የጋዜጠኝነት መርሆዎችን ብቻ አንጠልጥለው በመያዝ ሞያውን የበለጠ ያዘቅጡታል፡፡ እንደነዚህ ያሉ ሰዎች ሞያውን በተቀላቀሉ ቁጥር ገዢው ፓርቲ ይደሰታል፡፡ የጋዜጠኝነት መርሕ ተጥሶ ዘገባ ሲቀርብ የመናገርና የመጻፍ ነፃነት መብት በአገሪቱ ላይ መከበሩንና ጋዜጠኞቹ ግን ይህን መብት እንዴት እየተጠቀሙበት እንደኾነ ለዓለም ሕዝብ ለማሳያነት ይጠቀምበታል፡፡

በጋዜጠኝነት ዘርፍ ወደ ተለያየ የዓለም አገራት ተጉዘው ትምሕርት ቀስመው የመጡ ምሑራንም ስለ ጋዜጠኝነት ሞያ አስተያየት ሲጠየቁ ችግሩ ከሥሩ መርምረው ሞያው ነፃነት ያጣበትን ምክንያት ከእነ መፍትሔው በማስቀመጥ ለመቀየር ከመሞከር ይልቅ በነፃነት ዕጦት በኮሰመነው የግል ብዙኃን መገናኛ የሕትመት ውጤትና ጋዜጠኝነት ላይ ውርጅብኝ ያወርዱበታል፡፡ በከፍተኛ ትምሕርት ተቋማት የጋዜጠኝነትና ሥነ ጹሑፍ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ሳይቀሩ በአብዛኛው ለመመረቂያ ጹሑፋቸው የሚመርጡት ርእስና የሚሠሩት ጥናት የጋዜጠኝነትን ነፃነት የበለጠ የሚያሳጣ ነው፡፡
እነዚህ ኹሉ ችግሮች ተደማምረው ሞያውን አክስመውታል፡፡ አኹን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ጋዜጠኝነት ከእስር፣ከስደት፣ከፍረጃ፣ከፍርኃት የተረፈ ‹‹እስረኛ›› ጋዜጠኝነት ነው፡፡ ጋዜጠኝነት በአብዛኛው የራስ በራስ ቅድመ ምርመራ ራሱን ጠፍንጎ ባሰረ ባለሞያና ለሞያው የጠለቀ ዕውቀት በሌላቸው ሰዎች የመጨረሻ እስትንፋስ እየተንገታገተ ያለ ሞያ ነው፡፡ በመንግሥት በኩል ደግሞ ይቺኑ ትንሽ እስትፋስ እስከ መጨረሻው ለማጥፋት በሚደረገው ጫና ያሉት ጋዜጠኞች ሞያው የሚጠብቅባቸውን መረጃን ለሕዝብ የማስተላፍ ሥራን ከመሥራት ይልቅ ራስን ወደ መከላከል ሥራ ተሸጋግረዋል፡፡ በተለይ ካለፉት አራት ዓመታት ጀምሮ ያሉት ጋዜጦችና መጽሔቶች የፊት ገጽ ሽፋንና የድረ ገፆች ዋና መነጋገሪያ ርእስ ጋዜጠኞች ላይ የሚደረግ እስርና ጫና ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ይህ ደግሞ አንዱ የማዳከሚያ ስልት ሊኾን ይችላል፡፡

በየአራት ዓመቱ በሚካሄደውና ለሦስተኛ ጊዜ በተደረገው የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት መድረክ ላይ ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ተሳታፊ ኾና ቀርባ ነበር፡፡ ስብሰባው የሚደረገው በ197 የዓለም አገሮች መካከል ሲኾን ሲኾን አገራቱ የሰብዓዊ መብት አያያዛቸውን በሚመለከት ሪፖርት የሚያቀርቡበት እንዲኹም የሚቀርብባቸውን ወቀሳና ትችት አዳምጠው የሚያሳሽሉትን ‹‹አሻሽላለሁ›› የሚሉበት ያልተስማሙበትን ደግሞ ያልተስማሙበትን ምክንያት የሚያስረዱበት ስብሰባ ነው፡፡

ኢትዮጵያ በዚህ ስብሰባ ላይ በ2010 ላይ ስትሳተፍ የመጀመሪያዋ ቢኾንመ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮችን በሚመለከት 159 ጉዳዮችን እንድታሻሽል ተነግሯት ዘጠኛ ዘጠኙን መቀበሏን ስልሳውን ግን እንደማትቀበለው ተናግራ ነበር፡፡ስብሰባው በቀጥታ ከጄኔቭ በቴሌ ኮንፍረንስ የተመራ ሲኾን እያንዳንዱ አገራት ከሚገኙበት አገር ኾነው በስብሰባው እንደተሳተፉት ኹሉ ማክሰኞ ዕለት በተደረገውና ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ በተሳተፈችበት በዚህ የምክር ቤቱ ስብሰባ ላይም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ የተመራና ከአምስት በላይ የሚኒስቴር መስሪያ ቤት ምክትል ሚኒስትሮችን የያዘ ቡድን አዲስ አበባ በሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት ጽ/ቤት ተገኝተቶ በውይይቱ ተሳትፎ ነበር፡፡

በልኡካን ቡድኑ አማካኝነት የኢትዮጵያ ሪፖርት ከቀረበ በኋላ፤ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ፣ የበጎ አድራጎትና ማኅበራት ዐዋጅን በተለመከተና የፀረ ሽብር ሕጉን በሚመለከት በከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟታል፡፡ በስብሰባው ላይ የተሳተፉት አብዛኛው አገራት ኢትዮጵያ ላይ በሰጡት አስተያየት፤ኢትዮጵያ የፀረ ሽብር ሕጉን የመናገርና የመጻፍ ነፃነትን እንዲሁም የፖለቲካን ተቃውሞ ለማፈን እየተጠቀመችበት ስለኾነ ሕጉን እንድታሻሽልና ሕጉም ሲሻሻል የፖለቲካ ተቃውሞን ለማፈን እንዳትጠቀምበት ዋስትና የሚሰጥ መኾን እንዳለበት በመግለጽ ጠንካራ ወቀሳቸውን ሰንዝረዋል፡፡
የልኡካን ቡድኑ አባል የነበሩት የኮሚዩኒኬሽን ምክትል ሚኒስትሩ አቶ ሽመልስ ከማል በአገራቱ የቀረበውን ወቀሳ አጣጥለው፤ኢትዮጵያ ውስጥ በሽብር ሕጉ ሰበብ ተደርጎ የታሰረ አንድም ጋዜጠኛ እንደሌለ ጠንከር አድርው በመናገር የሽብር ተግባር ሲፈጽሙ ተይዘው የታሠሩና ከዚህ ቀደም በጋዜጠኝነት ሥራ ላይ ይሠሩ ነበር የሚባሉ እስረኞች ቢኖሩ እንኳን የታሰሩት ከጋዜጠኝነት ሞያቸው ጋር በተያያዘ ሳይኾን በፈጸሙት የሽብር ወንጀል መኾኑን አበክረው ተናግረዋል፡፡

አቶ ሽመልስ እንዲህ ያለ መከራከሪያ ሲያቀርቡ የመጀመሪያቸው አይደለም፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ አገር ውስጥ ያሉም የውጭ ጋዜጠኞች ሲጠይቋቸውም ይህንኑ ነው የሚመልሱት፡፡ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ሪፖርት ሲያወጡም የሚመልሱት ይህኑ ነው፡፡ አሁን ደግሞ የዓለም አገራት ተሰባስበው ኢትዮጵያ የመናገርና የመጻፍ ነፃነት አፈናን እንድታቆም፣በፖሊስ፣በመከላከያና በደህንንት ሰዎች የሚፈጸመው ‹‹ቶርቸር›› እንዲቆም ፀረ ሽብር ሕጉን ጋዜጠኞችን ለማሠር እንዳትጠቀምበት የዓለም አገራት ተሰባስበው ቢመክሩም የአቶ ሽመልስ ከማል ምላሽ ተመሳሳይ ኾኗል፡፡ በርካታ ችግሮችን ተቋቁሞ የሚውተረተረው የእስረኛው ‹‹ጋዜጠኝነት›› ትልቁ ፈታናም እዚህ ጋር ኾኗል፡፡ ጋዜጠኛ ይታሰራል ሲታሰር ደግሞ ‹‹በጻፈው ጹሑፍ ሳይኾን በሽብር ተግባር ላይ ስለተሳተፈ ነው›› የሚል ታፔላ ይለጠፍለታል፡፡ ይህ ደግሞ ሞያውን የበለጠ ችግር ውስጥ ይዘፍቀዋል፡፡ የ‹‹እስረኛው›› ጋዜጠኝነት ሌላ ፈተና ማብቂያ እንደተባለው ኢትዮጵያ የፀረ ሽብር ሕጉን፣ የመናገርና የመጻፍ ነፃነትን እንዲሁም የፖለቲካን ተቃውሞ ለማፈን እየተጠቀመችበት ነው በሚል እየተወቀሰችበት ያለውን ሕግ ስታሻሻል ይኾን?

የወያኔ ጥላቻ ፍሬ (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

$
0
0

መስፍን ወልደ ማርያም

ሚያዝያ 2006

mesfin n

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

ወያኔ ለትግራይ ሕዝብ ሀብትንና ብልጽግናን አመጣ ብለው የሚያምኑ ሰዎች ብዙ ናቸው፤ ወያኔ የሥልጣን ወንበሩ ላይ በመውጣቱ ትግሬዎች ሁሉ አልፎላቸዋል ተብሎ ይታመናል፤ በተለይ በአውሮፓና በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዚህ ላይ የጠነከረ እምነት አላቸው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ ውጭ ብዙ ውይይትም ይሁን ንትርክ ይደረጋል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ግን የተፈራ ርእስ ነው፤ ውስጥ-ውስጡን እንጂ አደባባይ አይወጣም፤ ይህንን ጉዳይ በኢትዮጵያ ውስጥ አደባባይ ለማውጣት ጊዜው የደረሰ ይመስለኛል፤ አረጋዊ በርሄ፣ ገብረ መድኅን አርአያ፣ አስገደ ገብረ ሥላሴ፣ አብርሃ ደስታ (አሥር ቢሞሉልኝ ደስ ይለኝ ነበር!) እየደጋገሙ ቢያነሡትም ሌሎች በቁም-ነገር የተቀበሉት አይመስልም፤ ሕዝቡ ግን በራሱ መንገድ እየተናገረና ምስክርነቱን እየሰጠ ነው፤ በመቀሌ የተሠራውን የመኳንንት መንደር ሕዝቡ አፓርቴይድ ብሎ ሲሰይመው፣ በአዲስ አበባ የተሠራውን መንደር መቀሌ ብሎ ሲሰይመው እየመሰከረ ነው፤ ‹‹የለሁበትም!›› እያለ ነው።

የትግራይ ሕዝብ መደህየቱ አልበቃ ብሎት ሲለምንም እየተሳቀቀ ነው፤ የሚለምነው ትግሬ ለብዙ ሰዎች ትግሬና ወያኔ አንድ መስሎ እንደሚታየው ያውቃል፤ አብዛኛው ሰው በወያኔ ላይ ያለውን ስሜት ያውቃል፤ ስለዚህም ሲለምን ሰዎች በወያኔ ላይ ያላቸውን ስሜት ስለሚያራግፉበት እየተሸማቀቀ ነው፤ አንድ የትግራይ ቄስ ከአርሲ ነኝ አሉኝና ለምን እውነቱን አይናገሩም ስላቸው እውነቱን ስናገር የማገኘው ስድብ ብቻ ነው አሉኝ፤ እኒህ ሰው ምን በወጣቸው የወያኔን ኃጢአት ተሸካሚ ይሆናሉ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በትግሬነቱ የተጠቀመ አለ፤ እኔ የማውቀው የደርግ ወታደር የነበረ ትግሬ ቆስሎ ከውትድርና ወጣና በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት የጥበቃ ሥራ ላይ ነበር፤ በጣም ይቸግረው ነበር፤ ሚስቱ ሕመምተኛ ነበረች፤ የቤት ኪራይ መክፈል ይቸገር ነበር፤ ዛሬ ግን የሚለብሰው ልብስ ሌላ ነው፤ ከኑሮውም ተርፎ ለሲጃራና ለጫት እያወጣ ነው፤ ወይም ሌሎች እያወጡለት ነው፤ ትግሬነታቸው ብቻ እንዲህ የደላቸው በጣም፣ በጣም ጥቂቶች ናቸው፤ ስለዚህም በወያኔ አገዛዝ ትግሬ ሁሉ ተጠቅሞአል ማለት ከጉልሁ እውነት ጋር የሚጋጭ ስሕተት ነው፤ አብርሃ ሰዎች ትግሬ ሁሉ ተጠቃሚ ሆኗል ሲሉ ‹‹ያመኛል›› ማለቱ ይገባኛል።

ወያኔ ትግሬ በመሆኑ ብቻ ትግሬ ሁሉ ዕዳ አለበት ማለት እንደወያኔ ማሰብ ነው፤ ወንጀል በዘር አይተላለፍም፤ እያንዳንዱ ሰው ለሠራው ሥራ ሁሉ ኃላፊነትን ይወስዳል፤ ጊዜው ሲደርስ ውጤቱንም ለመቀበል ይገደዳል፤ ይህ የሚሆነው ሰው ሁሉ በመንፈሳዊ ኃይል በጎ መንፈስ አድሮበት፣ አእምሮው በትምህርት ተገርቶ በትክክል ማሰብ ሲችል ነው፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁን በአለበት ሁኔታ በጎ መንፈስ የራቀው ይመስላል፤ አእምሮም ጭራሹኑ በእኩይ መንፈስና በጥላቻ እየዛገ ነው፤ ስለዚህ ያስፈራል፤ በደቡብ ሱዳን ሁለት መቶ ሰዎች በዘር ተለይተው ታረዱ ሲባል ያስፈራል፤ በናይጂርያ፣ በኮንጎ የሚካሄደውን የዘርና የሃይማኖት እልቂት ስንሰማ ያስፈራል፤ በ1997 ዓ.ም. መለስ ዜናዊና አዲሱ ለገሰ እንዳስታወሱን የሩዋንዳ የጎሣ እልቂት በብዙ ሰዎች አእምሮ ውስጥ አለ፤ የቅርብ ተኳሽ የሆነው የአግዓዚ ጦርም አድፍጦ መጠበቅ ያስፈራል፤ ሌላውም ይህንን አውቆ አድፍጦ መጠበቁ ያስፈራል፤ ሰማይ ጠቀስ የሠሩት፣ የሥልጣን ኃላፊነትን ችላ ብለው በሥልጣን የሚነግዱና የሚከብሩት፣ የማይኖሩበትን ሕንጻ የሚክቡት፣ ከሕዝብ ጋር ያላቸው የአይጥና የድመት ኑሮ ያስፈራል፤ አቶ አስገደ ወያኔ መደንገጡን ይነግረናል፤ መደንገጥ የማይቆጣጠሩት ፍርሃት ነውና አደጋ ያመጣል፤ አደጋው አደጋን ይጠራል፤ ይህም ያስፈራል።

በትግራይ ዙሪያ ያለው ምንድን ነው? የትግራይ ሕዝብ በየትኛው አቅጣጫ ነው አንደልቡ እየተዘዋወረ ለመሥራትና ለመኖር የሚችለው? ወያኔ የትግራይን ሕዝብ ከሰሜን ከወገኑ ከኤርትራ ሕዝብ ጋር ደም አቃብቶታል፤ በደቡብ-ምሥራቅ ከወሎ መሬት ቆርሶ የወሎን ሕዝብ ቂም አስቋጥሯል፤ በደቡብ-ምዕራብ ከጎንደር መሬት ቆርሶ የጎንደርን ሕዝብ ቂም አስቋጥሯል፤ የራስን ወገኖች አስቀይሞ ሱዳንን በመሬት ለመደለል የሚደረገው ጥረት ሁሉ ፋይዳ የለውም፤ ሱዳን ለራሱም ያልበጀ አገር መሆኑ እየታየ ነው፤ ወደፊት ደግሞ ይበልጥ ይታያል፤ በትግራይ ውስጥ ደግሞ ወያኔ የፈጠረው አፓርቴይድ የወያኔን የኑሮ ደረጃ ወደሰማይ ሲያስጠጋው፣ የቀረውን ወደአንጦርጦስ የደሀነት ገደል ውስጥ ከቶታል፤ በዚህም ምክንያት በአዲስ አበባ ከተማ ከነልጆቻቸው እየተዘዋወሩ የሚለምኑ ሞልተዋል፤ ይህ ልመናም ለወያኔ ለመገበር ነው፤ ብዙዎቹ እንደሚናገሩት የሚለምኑት የማዳበሪያ ዕዳቸውን ለወያኔ ለመክፈል ነው።

ወያኔ ከሀያ ዓመታት በላይ አፍንጫ እየያዘ ያስከፈለውን የሚመልስበት ጊዜ እየተቃረበ ነው፤ ጥያቄው ወያኔ እንዲመልስ የሚገደደው እንዴት ነው? የሚል ነው፤ጥላቻ ወደንዴት፣ ንዴት ወደቁጣ ተለውጦ ሲገነፍል ምጽዓት ደረሰ ማለት ነው፤ ሁሉም ሰው ራቁቱን ይሆናል፤ አንደአውሬ ከጥፍሩና ከጥርሱ በቀር ሌላ መሣሪያ አይኖረውም፤ ሰው ሁሉ በክፋት ወደአውሬነት ይለወጣል፤ ጠመንጃና ቦምብ አያገለግሉም፤ ሕንጻው ምሽግ አይሆንም፤ መኪናው፣ ባቡሩ፣ ታንኩ ከቆመበት አይነቃነቅም፤ የትም አያደርስም፤ ጭፍራ ሁሉ በየራሱ ፍዳ ታንቆ እንኳን ለሌላ ሊተርፍ ለራሱም የማይበቃ ይሆናል፤ ለነገሩ ጌታና ሎሌም የለም፤ ሁሉም በአውሬ እኩልነት የተፋጠጠ ነው፤ ርኅራኄ ተሟጦ፣ መግል ያዘለ ልብ ፈርጦ፣ ውይይትና ክርክር አብቅቶ፣ ጥርሱን ያገጠጠና ጥፍሩን የሳለ መንጋ በደም የሚራጭበት ሁኔታ ነው።

ሌላ አገር እንዲህ አልሆነም፤ እዚያ አገር እንዲህ አልሆነም፤ የሚባል ነገር የለም፤ እኛ ዘንድ ሌላ ነው፤ የኢትዮጵያ ደሀዎች እንባ የእግዚአብሔርን ሰማይ አጨቀየው!

ክፋት እንደእሳት ይቃጠላል፤ ኵርንችቱንና እሾሁን ይበላል፤ ጭፍቅ የሆነውንም ዱር ያቃጥላል፤ ጢሱም ተትጐልጕሎ እንደዓምድ ይወጣል፤ በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ቁጣ ምድር ተቃጥላለች፤ ሕዝቡም እሳት እንደሚበላው እንጨት ሆኖአል፤ ሰውም ለወንድሙ አይራራም፤ ሰው በቀኙ በኩል ይነቅላል፤ ይራብማል፤ በግራም በኩል ይበላል፤ አይጠግብምም፤ እያንዳንዱም የክንዱን ሥጋ ይበላል፤ ምናሴ ኤፍሬምን፣ ኤፍሬምም ምናሴን ይበላል፤… ኢሳይያስ 9/18-21

ትንቢተ ኢሳይያስ ለሩዋንዳውያን ብቻ አይደለም፤ ጥላቻና ክፋት በተዘራበት ቦታ ሁሉ ውጤቱ ጥፋት ነው፤ ምናሴ ኤፍሬምን በልቶ አይቀርም፤ ኤፍሬምም ምናሴን ይበላዋል።

ኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ በአምቦ ብጥብጥ የሁለት ሚሊዮን ብር ንብረት ወደመብኝ አለ

$
0
0
ከአዲስ አበባ ከተማ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው አምቦ ከተማ፣ በቅርቡ በተከሰተው ብጥብጥ ሰለባ ሆኛለሁ ያለው የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ ሁለት ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ንብረት እንደወደመበት አስታወቀ፡፡
744e

ከአዲስ አበባ ከተማ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው አምቦ ከተማ፣ በቅርቡ በተከሰተው ብጥብጥ ሰለባ ሆኛለሁ ያለው የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ ሁለት ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ንብረት እንደወደመበት አስታወቀ፡፡

የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ኃይለየሱስ በቀለ ባለፈው ዓርብ ለጋዜጠኞች እንደገለጹት፣ በአምቦ ቅርንጫፍ ውስጥ የሚገለገሉባቸው ቁሳቁሶች በሙሉ በእሳት ጋይተዋል፡፡ አቶ ኃይለየሱስ እንዳሉት፣ ብጥብጡ ከመነሳቱ ሦስት ሰዓት ቀደም ብሎ የብጥብጥ አዝማሚያዎች መስተዋላቸው ሪፖርት በመደረጉ ሠራተኞች፣ የጥበቃና የደኅንነት ሠራተኞች ባደረጉት ጥንቃቄ 1.3 ሚሊዮን ብርና በዕለቱ ሲሠራባቸው የነበሩ ሰነዶች በገንዘብ ካዝና ውስጥ እንዲገቡ በመደረጉ ከጉዳት ተርፈዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም አንድ ጥበቃ እሳቱ በተነሳበት ወቅት ከመስኮት ሲዘል እግሩ ላይ ጉዳት ከመድረሱ በስተቀር ሠራተኞች ጉዳት እንዳልደረሰባቸው ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል፡፡

ሚያዝያ 22 ቀን 2006 ዓ.ም. ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ለተቃውሞ ሲወጡ፣ ወደ ከተማው በዘለቀው ብጥብጥ በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ በርካታ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል፡፡

መንግሥት ባወጣው መግለጫ በአምቦና በኬኩታዮ ከተሞች የሰባት ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ፣ የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክን ጨምሮ፣ በተለያዩ መንግሥታዊና የግል ተቋማት ንብረቶች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡

የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ የሚገለገልበት ንብረትነቱ የአቶ ተስፋዬ ተስፋ ሕንፃ ላይ የተነሳው የእሳት ቃጠሎ፣ ከሕንፃው ፊት ለፊት በተቃጠለ ከባድ ተሽከርካሪ መነሻ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት መኖሩን አቶ ኃይለየሱስ ተናግረዋል፡፡

የተነሳውን ብጥብጥ መንግሥት ሙሉ በሙሉ እንደተቆጣጠረው በማስታወቁ፣ ባንኩ ያቋረጠውን ኦፕሬሽን በድጋሚ ለመጀመር እየተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል፡፡

ነገር ግን ባንኩ የነበረበት ሕንፃ የተቃጠለ በመሆኑና ለዕድሳት ተጨማሪ ጊዜ የሚፈልግ በመሆኑ፣ ሌሎች አመቺ ሕንፃዎችን ለመጠቀም የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ  መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡

የባንኩ አምቦ ቅርንጫፍ በ2003 ዓ.ም. ሥራ የጀመረ ሲሆን፣ 468 ደንበኞች አሉት፡፡ ቅርንጫፉ አዲስ እንደመሆኑ ከዋናው መሥሪያ ቤት ጋር በኔትወርክ እንዳልተገናኘ የሚናገሩት አቶ ኃይለየሱስ፣ በሠራተኞቻቸው ጥረት ግብይት ይካሄድባቸው የነበሩ ጠቃሚ መረጃዎች መትረፋቸውን ተናግረዋል፡፡ ሚያዝያ 29 ቀን 2006 ዓ.ም. አቶ ኃይለየሱስ የመሩት የልዑካን ቡድን በአምቦ ከተማ በመገኘት ጉዳት የደረሰበትን ቅንጫፍ ጎብኝቷል፡፡

ጉዳዩን ተራ ብጥብጥ አድርጐ መመልከት ያልወደደው መንግሥት፣ ከብጥብጡ ጀርባ አሉ ባላቸው ኃይሎች ላይ ዕርምጃ እንደሚወስድ እያስታወቀ ነው፡፡ የኢትዮ-ጂቡቲ

የባቡር መስመር ዝርጋታ ጅማሮ፣ ለማብሰር ባለፈው ሳምንት ድሬዳዋ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከአገር ሽማግሌዎች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በተነጋገሩበት ወቅት እንዳሉት ከጉዳዩ ጀርባ ባሉ አካላት ላይ መንግሥት ዕርምጃ ይወሰዳል፡

15 Health Benefits of Eating Apples (Amharic Video)

$
0
0


What makes apples so great?

In 2004, USDA scientists investigated over 100 foods to measure their antioxidant concentration per serving size. Two apples—Red Delicious and Granny Smith—ranked 12th and 13th respectively. Antioxidants are disease-fighting compounds. Scientists believe these compounds help prevent and repair oxidation damage that happens during normal cell activity. Apples are also full of a fibre called pectin—a medium-sized apple contains about 4 grams of fibre. Pectin is classed as a soluble, fermentable and viscous fibre, a combination that gives it a huge list of health benefits.
15 Health Benefits of Eating Apples (Amharic Video)

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live