Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ዜና ዘ-ትግራይ (አብርሃ ደስታ ከመቀሌ)

$
0
0

አንድ፡ አድዋ

Abrham Destaበትግራይ አድዋ ወረዳ የሚገኙ ሦስት የአልመዳ ፋብሪካዎች (አልመዳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ፣ አልመዳ ልብስ ስፌት ፋብሪካና (አልመዳ) ሳባ እምነበረድ ፋብሪካ) የኬሚካል ቆሻሻ (Chemical Residue) የሚጠራቀምበት ከመሬት በታች የሚገኝ ጋን ፈንድቶ ወደ ላይ በመተኮሱ የአከባቢ ብክለት አስከትሏል። ይህንን የቆሻሻ ኬሚካል ማጠራቀምያና ማጣርያ ፍንዳታ አደገኛና መርዘኛ ሽቶ በመፍጠሩ በአከባቢው (እስከ አስር ኪሜ ራዲያስ ድረስ) የዉሃና የአየር ብክለት አስከትሎ በሰዎችና እንስሳት የመታመም ምልክቶች እየታዩ ነው። ይባስ ብሎ ደግሞ የፋብሪካዎቹ ሰራተኞች (ከ 500-600 የሚደርሱ) ችግሩ ተቋቁመው እንዲሰሩ ስለ ተገደዱ የጤና ችግር እንዳያስከትልባቸው በመስጋት ለትግራይ ክልል መንግስትና ለትእምት ሓላፊዎች አቤት ያሉ ሲሆን እስካሁን ግን መልስ አላገኙም። መንግስት መፍትሔ እንዲሰጣቸው ተማፅነዋል።

ሁለት፡ ታሕታይ ማይጨው

በትግራይ ክልል፡ ማእከላዊ ዞን፣ ታሕታይ ማይጨው ወረዳ (ከሁለት ሳምንት በፊት ነው) የመንግስት ሰራተኞች ከህወሓት ሓላፊዎች ጋር አለመግባባት ፈጥሯል። በወረዳው ወደ 650 የሚሆኑ አስተማሪዎች፣ 420 የግብርና ሰራተኞች፣ ከ300-350 የጤና ሰራተኞችና ከ550 በላይ የወረዳው የመንግስት አስተዳደር ሰራተኞች የኢኮኖሚ ጥያቄ አስነስተዋል። እነኚህ ሰራተኞች የወር ደመወዛቸው አነስተኛ ሁኖ ሲያበቃ (ግብር ሲቆረጥበት የባሰ እንደሚያንስ ነው) ተጨማሪ ወጪ ስለበዛባቸው መኖር አስቸጋሪ እንደሆነባቸው ገልፀዋል።

ደመወዛቸው አነስተኛ፤ ከዚህ የመንግስት (የማይቀረውን) ግብር ይቆረጣል፣ የህወሓት የአባልነት መዋጮ ይቆረጣል፣ የትግራይ ልማት ማህበር (TDA) ይቆረጣል፣ የአባይ ግድብ ይቆረጣል፣ (የቀይ መስቀል የሚቆረጥባቸውም አሉ) ወዘተ … ። በቃ መቁረጥ ነው። ተጣርቶ እጃቸው የሚገባ በጣም ትንሽ ብር ነው። በትንሽ ብር (ከንሮ ውድነቱ ጋር ተደምሮ) ህይወት ለነሱ መከራ ሁናለች።

ችግራቸው ለዞኑ አስተዳደር ለማስረዳት ሞክረዋል። ‘ወጪ በዝቶብናል’ አሉ። አስተዳዳሪውም ‘የመንግስት ትእዛዝ ነው’ አለ። እንሱም ‘ቢያንስ የህወሓት አባልነት መዋጮ ይቀነስልን’ አሉ። አስተዳዳሪውም ‘ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ የህወሓት አባል መሆን አለበት፤ አለበለዝያ ግን ከስራው ይባረራል’ ብሎ አስፈራራቸው። አሁን ተስፋ በመቁረጥ ላይ ናቸው።

ሦስት፥ ሽሬ

በሽሬ አከባቢ ከፍተኛ የሆነ የውሃ ችግር መኖሩ ለማወቅ ችያለሁ። ከሩቅ ቦታ የሚመጣው የጉድጓድ ውሃ (ንፁህ ያልሆነ ውሃ) በብዙ ብር ይገዛል። አብዛኞቹ የሽሬ ሆስፒታል ታካሚዎች በውሃ ወለድ በሽታዎች የሚሰቃዩ መሆናቸው መረጃ ደርሶኛል። በአከባቢው ከዓመታት በፊት በእስራኤላውን ባለሙያዎች የተጠና የውሃ ቁፋሮ ተደርጎ እንደነበርና በሙስና ምክንያት ውጤታማ ሳይሆን ቀርቶ እስካሁን ድረስ የዉሃ ችግሩ እንዳለ ነው።

አራት፡ የትግራይ መንግስት ፕላን

የትግራይ መንግስት በግብርና ዘርፍ ለውጥ ለማምጣት የመስኖ እርሻ ለማስፋፋት ብዙ ዉሃ ለማቆር የሚያግዙ ቁፋሮዎች አከናውነዋል። ብዙ የዉሃ ጉድጓዶች ተቆፈሩ። ውሃ ተጠራቀመ። አርሶ አደሮች በዓመት ሁለቴ ማፍራት እንዲችሉ ምርጥ ዘርና መዳበርያ (fertilizer) በብድር እንዲወስዱ ተገደዱ (ካልወሰዳቹ መሬታቹ ለሌላ ሰው አሳልፈን እንሰጠዋለን በሚል)። አርሶ አደሮቹ ተበድረው ወሰዱ። ተጠቀሙበት። እህሉ ሳይደርስ የቁፋሮውን ውሃ ደረቀ። ፍሬ ሳይሰጥ ቀረ። ብድሩ ግን አለ። ከሰኔ ወር በፊት ብድሩ መመለስ አለባቸው። ከየት አምጥተው ይከፍሉታል? አርሶ አደሮቹ ተጨናንቋል።

አንድ ነገር ሲተገበር መጀመርያ በጥናት የተደገፈ መሆን አለበት።


አቡነ ማቲያስና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በዓባይ ወንዝ ዙሪያ ትልቅ የቤት ሥራ ይጠብቃቸዋል

$
0
0

ጸሐፊው በፍቅር ለይኩን (በሪፖረተር ጋዜጣ እንዲወጣ ካደረጉ በኋላ ለዘ-ሐበሻም እንደላኩት)

አቡነ ማቲያስ

አቡነ ማቲያስ

በቅርቡ ሙስጠፋ አል ላባድ የተባለ ሊባኖሳዊ ፖለቲከኛና ጸሐፊ Egypt is Battling Ethiopia over the Nile Water በሚል ርዕስ አንድ መጽሐፍ አሳትሞ አውጥቷል፡፡ ይህን የአል ላባድን መጽሐፍ ‹‹አስ ሳፊር›› የተባለ የሊባኖስ ዕለታዊውና ተነባቢ የዐረብኛ ጋዜጣ የመጽሐፉን አጭር ዳሰሳ በፊት ለፊት ገጹ ይዞ ወጥቶ ነበር፡፡ ራኒ ጌሃ የተባለ ጋዜጠኛም የሊባኖሱን ‹‹አስ ሳፊር›› ጋዜጣ ዳሰሳ Egypt and Ethiopia Heading Toward a War Over Water በሚል ርዕስ በእንግሊዘኛ አሳትሞ ወሬውን ለዓለም መገናኛ ብዙኃን አድርሶታል፡፡

ሊባኖሳዊው ጸሐፊ በመጽሐፉ ግብፅ በናይል ወንዝ ላይ ያላትን ጥንታዊና ሺሕ ዘመናትን ያስቆጠር፣ ታሪካዊና ሕጋዊ የሆነ ልዑላዊ መብቷን በመጋፋት ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ በአፍሪካ ተወዳዳሪ የሌለው ግዙፍ የሆነ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ እየገነባች ነው በማለት የተለመደውን ውግዘትና ማስፈራራት የተንጸባረቀበት የሚመስል እሳቤውን በመጽሐፉ በሰፊው አካቶታል፡፡

ጸሐፊው ይህ ኢትዮጵያ በመገንባት ላይ ያለችው ግዙፍ ግድብ ‹‹በግብፃውያን ጉሮሮ ላይ የመቆም ያህል ነው፡፡›› ሲል በቁጣና በእልኽ ስሜት ውስጥ የገባ በሚመስል ሁናቴ ነው የገለጸው፡፡ ይኽም ይላል ሙስጠፋ አል ላባድ 97.5 በመቶ በረሃማ ለሆነችው ግብፅ፣ ዓለምን እጹብ ድንቅ ላሰኘው ለግዙፍ ሥልጣኔዋ፣ ወርቃማ ለሆነው ታሪኳ፣ ክብርና ኩራቷ እንዲሁም 90 ሚሊዮን የሚሆነው የግብፅ ሕዝብ ሁለተናዊ ሕይወት ቁልፍ በሆነው በዚህ ታሪካዊ ወንዝ ላይ ኢትዮጵያ የጀመረችው የኃይል ግንባታ ለግብፃውያን አስጊ መሆኑን ነው የገለጸው ላባድ በመጽሐፉ ውስጥ፡፡

ይኸው ጸሐፊ ግብፅ፣ ሱዳንና ብሪታኒያ የተዋዋሉትን የ1950 ስምምነት በማንሣት ግብፅ በዓባይ ወንዝ ላይ ያላትን መብት ማንም ሊጋፋው የማይችል ታሪካዊና ሕጋዊ መብቷን መሆኑን አስረግጦ ሊያስረዳንም ሞክሯል፡፡

ላባድ በተጨማሪም የታችኛዎቹ የተፋሰሱ አገራት የሆኑት ግብፅና ሱዳን በተናጠል ከእንግሊዝ ጋር ያደረጉትን ስምምነት ሕጋዊ እውቅና በመስጠት ይደግፋል፡፡ በአንፃሩ ደግሞ በላይኛዎቹ ተፋሰስ አገራት በኢትዮጵያ አስተባባሪነት በናይል ወንዝ ላይ ፍትሐዊ የሆነ የውኃ አጠቃቀም እንዲኖር ያደረጉትን የኢንተቤውን ስምምነት በማንሣት ኢትዮጵያ በላይኛዎቹ ተፋሰስ አገራት መካከል ያደረገችውን ስምምነት በተመለከተ ሲናገር ‹‹ኢትዮጵያ ግብፅን በጉልበት ለማስፈረም አትችልም፤›› ሲል ይደመድማል፡፡

ይህ ስምምነትና ይላል ላባድ ግብፅ እስከሌለችበትና እስካልተስማማች ድረስ ዋጋ የሌለው ወረቀት ላይ ብቻ ፉከራ ነው የሚል አንድምታ የተንጸበራቀበት አቋሙን ለመግለፅ ሞክሯል በዚሁ መጽሐፉ፡፡

ሙስጠፋ አል ላባድ ግብፅ ወይም ግብፃውያን ዘወትር የማያንቀላፉ፣ ንቁ የሆነና በተጠንቀቅ የቆሙ ሁለት ዓይኖች አሏት፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ትልቁና ዋንኛው ዓይኗ ሁሌም በዓባይና በዓባይ ዙሪ ላይ እንደተተከለ ነው፡፡ ሌላኛው ዓይኗ ደግሞ በመካከለኛው ምስራቅና በባሕረ ሰላጤው እንደሚያማትር ጽንፈኝነት የተጫነው በሚመስል አገላለጽ ሊያስረዳን ይዳደዋል፡፡

እናም ሙስጠፋ ግብፅና ግብፃውያን በዓባይ ዙሪያ ላይ ምን ያህል ስሱና ቀልድ የማያውቁ መሆናቸውንም ሊነግረን ይሞክራል፡፡ ይኸው ሊባኖሳዊ ጸሐፊ ኢትዮጵያ ይህን ያህል ግዙፍ የሆነና በአፍሪካ ተወዳዳሪ የሌለው የኤሌክትሪክ ማመንጫ ኃይል ለመገንባት ያነሳሳት ምክንያቶች በማለት ስድስት ዐበይት ምክንያቶቹን በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ይተነትናል፡፡ ወደእነዛ የሙስጠፋ አል ላባድ ትንታኔዎች ለመግባት አልሻም፡፡

ነገር ግን ሊባኖሳዊው ጸሐፊ ሙስጠፋ አል ላባድ በዚህ መጽሐፉ ውስጥ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የጀመረችውን ግዙፍ ግንባታና ይኽን ተከትሎም ከናይል ተፋሰስ አገራት በዋነኝነት ደግሞ ከግብፅ ጋር የገባችበትን ፍጥጫና የጀመረችውን ውይይት/ድርድር ፈር ለማስያዝ ግብፅ ምን ዓይነት ውሳኔ ልትወስድ እንደምትችል የሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ነው ይለናል፡፡

ነገር ግን ይላል ሙስጠፋ ማብራሪያውን ሲቀጥል ግብፅ ለወደፊቱ የምትወስደውን እርምጃ ምንም ይሁን ምን የምናየው ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ግን ግብፅ ይህን ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የጀመረችውን ግዙፋ ግንባታ ለማስቆም መውሰድ ካለባት እርምጃ መከካል ብሎ በግንባር ቀደምትነት ከጠቀሳቸው ምክንያቶቹ መካከል ሲጠቅስም፡-

ግብፅ በዓባይ ወንዝ ላይ ያላትን ‹‹የማይለወጥና የማይሻር›› ታሪካዊ፣ ሕጋዊና ሉዓላዊ የሆነ ጥቅሟን ለማስከበር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሺሕ ዘመናት እናት በሆነችው በግብፅ ኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን በኩል ከፍተኛ የሆነ ጫና ማሳደር የምትችልበትን አማራጭ ማየት ይገባታል በማለት አበክሮ ይገልጻል፡፡

ሙስጠፋ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የጀመረችውን ልማት በግብፃውያን ሕልውና ላይ የመፍረድ ያህል ነው ብሎ ለሚሟገትላት ግብፅ ለዚህ የሞት ሽረት ጥያቄ ያለ ምንም ልዩነት ሁሉም ግብፃዊ ሊነሣ እንደሚገባው ይወተውታል፡፡ እናም በዚህ የሞት ሽረት ዲፕሎማሲያዊ ትግል ግብፅና ግብፃውያን ያላቸው ተስፋ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በኩል ብቻ እንደሆነ ለግብፅና ለግብፃውያኑ አበክሮና አስረግጦ ገልጧል፡፡

በእርግጥ ግብፃውያን በሃይማኖት ወዳጃቸው በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በኩል የተቻላቸውን ያህል ጥረት ሊያደርጉ እንደሚችሉ እርግጥ ነው፡፡ ለዚህ ጥሩ ማሳያ የሚሆነን ባለፈው ወርኻ ክረምት የግብፅ ሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ አባልና አዲሱ የግብፅ ፕሬዝዳንት የሆኑት መሀመድ ሙርሲ ለአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ወደ መዲናችን አዲስ አበባ መጥተው በነበሩበት ጊዜ ከነፍሰ ሔር ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸውን በይፋ ከመገናኛ ብዙኃን አይተናል፣ አድምጠናል፡፡

ይህ የመሀመድ ሙርሲ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ያደረጉት ጉብኝትና ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ጋር ያደረጉትን አጭር ቆይታ እንደ አንዳንድ ተንታኞች ሁለት ዐበይት ምክንያቶች ሊኖረው እንደሚችል ተገልጾ ነበር በወቅቱ፡፡

የመጀመሪያው በሁለቱ አገራት ማለትም በግብጽ ኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያንና በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በኩል ለሺሕ ዘመናት ለዘለቀው ታሪካዊ ግንኙነት ክብርና እውቅና መስጠት ሲሆን፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ጥንታዊና ታሪካዊ የሆነ የሁለቱ አገራትና አብያተ ክርስቲያናትን ግንኙነት አስታኮ በጥንታውያኑ ኢትዮጵያውያን ነገሥታት ዘመን በኢትዮጵያ በኩል በእናት ቤተ ክርስቲያናቸው በግብጽ ኮፕቲክ ክርስቲያን ወንድሞቻቸው ላይ ይደረስ ለነበረው በደልና ግፍ እንደማስፈራሪያ ሆኖ በቆየውና ለግብፃውያን ሕልውና መሠረት በሆነው በዓባይ ወንዝ ላይ የተንጠለጠለ እንደሆነ ነው፡፡

ምናልባትም ሌላኛው ምክንያት በዘመነ ሆስኒ ሙባረክ አንፃራዊ በሆነ መልኩ የተረጋጋ ሕይወት አላቸው የሚሉት ግብፃውያኑ ክርስቲያኖች የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ ባልተጠበቀ ሁናቴ ወደ ግብፅ ፖለቲካ ማማ ላይ መውጣቱ በግብፃውያኑ ክርስቲያኖች ላይ ምንም ዓይነት የተለየ ጫና፣ ግፍና መከራ እንደማይደርስባቸው ዋስትና ወይም ማረጋገጫ የመስጠት ዓይነት እንደሆነ ትርጉም ተሰጥቶታል፡፡

ይሁን እንጂ የመሀመድ ሙርሲ ጉብኝትና ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ጋር ያደረጉት ውይይት ዐቢይ አጀንዳ ግን የዓባይ ውኃ ጉዳይ መሆኑን ለመናገር ነቢይ ወይም ወልይ መሆን የሚያስፈልገው ነገር አይመስለኝም፡፡ እናም መሀመድ ሙርሲ ወደ ስልጣን በመጡ ማግሥት በአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ሰበብ ይህን የግብፅንና የግብፃውያንን ቁልፍ አጀንዳ፣ የዓባይን ጉዳይ ከግብፅ ጋር ቆየና ታሪካዊ ግንኙነት ባላት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጠረጴዛ ላይ ማስቀመጣቸው፣ ለቤተ ክርስቲያኒቱ የአደራ መልእክትና ትልቅ የቤት ሥራ መስጠታቸው እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡

ይህን ከላይ በአጭሩ ለመግለጽ በሞከርኩት የሙስጠፋ አል ላባድ መጽሐፍ ውስጥ ግብፅና ግብፃውያን በዓባይ ውኃ ላይ ለመደራደር ያላቸው ተስፋ ‹‹በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲየን በኩል ብቻ ነው፡፡›› የሚል አንድምታ ያለው ምክሩና ከሰሞኑ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባትና መንፈሳዊ መሪ የሆኑት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ባስተላለፉት ቃለ ቡራኬ ስለ ዓባይ ውኃ ጉዳይ ያነሡት ቁም ነገር ለዚህ አጭር መጣጥፍ መነሻ ሆነኝ፡፡

በመላው በክርስትና ሃይማኖት አማኞች ዘንድ ባለፈው ሳምንት የተከበረውን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤ በዓል አስመልክተው፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የሆኑት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ በአገር ውስጥና በውጭ አገር ለሚገኙ መንፈሳዊ ልጆቻቸው ቡራኬና ቃለ በረከት አስተላልፈው ነበር፡፡

ቅዱስ ፓትርያርኩ ባስተላለፉት በዚህ በቃለ በረከታቸውና በቡራኬያቸውም፡- ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ሁሉ የዘመናት እንቆቅልሽ ሆኖ በቆየ በአንድ ወቅታዊ፣ አንገብጋቢና እጅግ ወሳኝ በሆነ አገራዊ አጀንዳ ላይ ፍጹም አዎንታዊነት፣ የድልና በእግዚአብሔር አምላካችን ኃይል ሁሉ ይቻለናል የሚል እምነትና ጽናት በተንጸባረቀበት በሚመስል፣ በትንሣኤው በዓል ‹‹የእንኳን አደረሳችሁ!›› የመልካም ምኞት መግለጫቸው ለኢትዮጵያውያን ሁሉ አንድ ዐቢይ የሆነ መልእክትን አስተላልፈዋል፡፡

ይኸውም ኢትዮጵያ አገራችን በእግዚአብሔር ከአምላኳ በተቸራት በጥንታዊውና በታሪካዊ ወንዟ በዓባይ ላይ የጀመረችው ታላቁ የሕዳሴው ግድብ ያለ ምንም ጥርጥር በድል ተጠናቆ፣ ለፍሬ በቅቶ፣ ‹‹ከዓባይን ልጅ ውኃ ጠማው›› ተረት ወጥተን ከዓባይ በረከት ጠጥተን የምንረካበት መልካምና ብሩኅ ዘመንን ኢትዮጵያውያን ሁሉ በዓይናቸው እንደሚያዩት ቅዱስነታቸው ያላቸውን ጽኑና የማያወላውል ተስፋቸውን ገልጸዋል፡፡

ቅዱስነታቸው በዚህ መልእክታቸውም ለሕዳሴው ግድብ መጠናቀቅ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ባለበትና በተሰማራበት የሥራ መስክ ሁሉ በአገር ፍቅር ስሜት፣ በአንድነትና ጠንካራ የሥራ መንፈስ የበኩሉን እገዛና ርብርብም እንዲያደረግም ነው ያሳሰቡት፡፡

የቅዱስ ፓትርያርኩ ይሄ መልእክታቸው በአንዳንዶች ዘንድ እምብዛም የተወደደላቸው አይመስልም፡፡ እንደውም እነዚሁ ይህ የፓትርያርኩ መልእክት ያላስደሰታቸው በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ አንዳንድ ኢትዮጵያውን ወገኖቻችን ይህች በመንግሥት ተቀንብባ ለፓትርያርኩ አንደበት ለሕዝብ ይደርስ ዘንድ የተላላፈች ‹‹ኢህአዴጋዊ›› መልእክት ናት በማለት የሰላ ትችታቸውን ሰንዝረዋል፡፡

እርሳቸው የሃይማኖት አባት ናቸው እንጂ የመንግሥት አፈ ቀላጤ አይደሉም፡፡ እናም በዚህ በትንሣኤው በዓል ላይ ማስተላለፍ የሚገባቸው መልእክት እኛ የሰው ልጆች ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ ሞትና ትንሥኤ ስለተጎናጸፍነው ነጻነት፣ ድል፣ በረከትና የዘላለም ሕይወት እንጂ ስለ መንግሥት የፖለቲካ አጀንዳ መሆን አልነበረበትም በማለት ቅሬታቸውን በጓዳም በይፋም ሲገልጹ ተሰምተዋል፡፡

በበኩሌ ግን ከትንሣኤው ኃይልና ተስፋ፣ መንፈሳዊነት ተቀዳሚና ዋና አጀንዳነት ባሻገር ይህ በዓባይ ወንዝ ላይ የተጀመረውን የታላቁን የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ በማስመልከት ቅዱስ ፓትርያርኩ 40 ሚሊዮን ለሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ምእመኖቻቸው ያስተላለፉት መልእክት የመንግሥት ፖለቲካዊ አጀንዳ ነው የሚያስብለው ምክንያት ብዙም አይዋጥልኝም፡፡

አገራችን ከድህነት፣ ከልመና፣ ከራብ፣ ከስደት፣ ከተመጽዋችነት… ወዘተ የምትወጣበትና እኛም ሕዝቦቿም ለጥ ብለን ከተኛንበት የስንፍና ፍራሽ ላይ አቅንቶ የሚቀሰቅሰን ሁለተናዊ የሆነ የትንሣኤው አዋጅ መለከት በብርቱ እንደሚያስፈልገን ጥያቄ የለውም፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ ዕለት ለአገራችንም ሆነ ለሕዝባችን ሁለተናዊ የሆነ ትንሣኤ እንደሚያሰፈልገው ማወጅ የአንድ መንፈሳዊ አባት ተግባርና ኃላፊነት እንደሆነ ነው አጥብቄ የማምነው፡፡

ብሔራዊ ጥቅማችን፣ የአገራችንን ነፃነት፣ ልዑላዊነትና አንድነት በተመለከተ ቤተ ክርስቲያናችን እንደ ትላንትናው ሁሉ በቃልም በተግባርም የነበራትን ወሳኝ ሚናና ተሣትፎ በተመለከተ ዛሬም ድምፅዋን ከፍ አድርጋ ማሰማቷ አዲስ ነገር አይደለም፡፡ ትላንትና ያደረገችው፣ ዛሬም ልታደርገው የሚገባና ወደፊትም አጽንታ ልትቀጥልበት የሚገባው መልካም የሆነ ክርስቲያናዊ ባህል ነው የሚመስለኝ፡፡

ስለሆነም የዓባይ ጉዳይ በማንም ይነሳ በማንም አንድ የማምንበት እውነት ግን አለ፡፡ ይኸውም የዓባይ ጉዳይ ብሔራዊ አጀንዳችን፣ የሁላችንም ጉዳይ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ፡፡ በአንድ የታሪክ ወቅት ታይተው የሚያልፉ የአንድ መንግሥት ወይም የአንድ ፓርቲ ጉዳይ አይደለም፡፡ ሊሆንም አይችልም፡፡ ዓባይና የዓባይ ጉዳይ ዘርን፣ ጎሳን፣ ሃይማኖትን ሳይለይ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ አንገብጋቢ ጉዳይ እንጂ፡፡

በዓባይ ጉዳይ ላይ ንጉሡ ቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ፣ በርካታ ኢትዮጵውያን ምሁራንና ዲፕሎማቶች ያደረጉት በርካታ የሆኑ ጥረቶችና ልፋቶች ነበሩ፡፡ የደርግ መንግሥት እንዲሁ የበኩሉን ያላሰለሰ ጥረት አድርጓል፣ ለፍቷል፡፡ ዛሬ እነዚህ መንግሥታት አልፈው ታሪክ ሆነዋል፡፡ ኢትዮጵያችን ግን ዛሬም አለች፣ ወደፊትም ትኖራለች፡፡ ዓባይ ወንዛችንም ትላንትና ነበር፣ ዛሬም አለ፣ ወደፊትም ይኖራል፡፡

የኢህአዴግ መንግሥትም በለስ ቀንቶት ይህ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያን ሁሉ የዘመናት እንቆቅልሽ የሆነውን ዓባይን ጉዳይ ከወረቀት አጀንዳነት ወደ መሬት በማውረድ በታሪካችን በአፍሪካ ትልቅ የሆነውን ሕዳሴውን ግድብ እውን ለማድረግ የበኩሉን ተግባራዊ ጥረት እያደረገ ነው፡፡ ኢህአዴግም እንደ ትላንትናዎቹ የኃ/ሥላሴና የደርግ መንግሥታት ያልፋል፣ አንድ ቀን እንደ ሸማም ተጠቅልሎ በታሪክ ማኅፀን ውስጥ በተራው ይገባል፡፡ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውን ግን ዛሬም፣ ሁሌም ይኖራሉ!!

ከጥንት ዘመን ጀምሮ ኢትዮጵያ ነበረች፣ ዓባይም ነበር፡፡ ኢህአዴግ ገና ሳይታሰብ፣ ሳይጸነስና ሳይኖርም በፊት ዓባይ ይፈስ ነበር፣ ዛሬም በፊታችን እየፈሰሰ አለ፣ ወደፊትም ሲፈስ ይኖራል፡፡ መንግሥት ዓባይን በየትኛውም መልኩ ቢሆን የራሱን ፖለቲካዊ አጀንዳ ማስፈጸሚያ፣ ዕድሜ ማራዘሚያና ጊዜያዊ የፖለቲካዊ ትርፍ ማጋበሻ አደረገውም አላደረገውም ዓባይን በማልማት ረገድ ግን ከአሁን ወዲያ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ወደኋላ የምንመለስበት ጉዳይ ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡ ለምን ቢባል የዓባይ ጉዳይ በእኛ ዘመን የህልውናችን፣ የመኖርና ያለ መኖር ጥያቄ ሆኖ ከፊታችን ተድቅኗልና፡፡

ስለሆነም በዓባይ ወንዝ ላይ የሚካሄድ ማንኛውንም ዓይነት ልማትን በተመለከተ የሃይማኖት አባቶቻችንም ሆኑ ባለ ሥልጣኖቻችን ከሚነግሩን በላይ በተግባር አንደበት፣ በፍቅርና በአንድነት መንፈስ እጅ ለእጅ ተያይዘን ልንወጣው የሚገባን ታላቅ የሆነ የቤት ሥራ ገና ከፊታችን እንዳለን ነው የሚሰማኝ፡፡

በዚህ ረገድ ደግሞ ከዓባይ ወንዝ ጋር በተያያዘ ታላቅ የሆነ ታሪካዊ ሚና የነበራትና ያላት ጥንታዊቷና ሐዋርያዊቷ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን፣ መንፈሳዊ አባቶችቻንና መሪዎቻችን እንዲሁም እኛ ክርስቲያኖች ሌላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያለ ምንም ልዩነት በማስተባበር ገና በተግባር ልንወጣው የሚገባ ትልቅ የቤት ሥራ በፊታቸው ተደቅኖ እንዳለ ይሰማኛል፡፡

ይህ አጭር መጣጥፍም ቤተ ክርስቲያናችን፣ መንፈሳዊ አባቶቻችንና መሪዎቻችን እንዲሁም እኛንም ጨምሮ ዓባይ ወንዛችንን በተመለከተ ከቃል ባለፈ በተግባር ልንወጣው የሚገባ ትልቅ የቤት ሥራ ከፊታችን ተዘርግቶ እንዳለ በቅንነት መንፈስ ለማሳሰብ ነው፡፡ በተጨማሪም ቤተ ክርስቲያናችን በቀደመ ታሪክ ዘመኗ የዓባይ ወንዝን በተመለከተ የነበራትን ወሳኝ ሚና ከታሪክ ማሕደር በመፈተሸና አሁን ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በማያያዝ የበኩሌንና የተሰማኝና ጥቂት ነገር ለማለት ነው ብዕሬን ያነሳሁት፡፡

ግብፃውያኑ በመንፈሳዊነት ስም ባቀነባበሩት፣ የፈጠራ ተረት ተረት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ለ1600 ዘመናት በግብፃውያኑ ኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን የባርነት ቀንበር ውስጥ ወድቃ ስትማቅቅ እንደነበር የታሪክ መዛግብቶቻችን ይጠቁማሉ፡፡ ይህ ሐቅም የቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ አጥኚዎችና የሥነ መለኮት ምሁራኖቿም ሳይቀሩ የሚመስክሩት ነው፡፡

እነዚህ በአፍሪካና በመላው ዓለም ባለፉት ሺሕ ዓመታቶች ባስመዘገቡት ድንቅና ኃያል ሥልጣኔያቸው የተነሣ በዓለም መድረክ እንደ ብርቅ የሚታዩ ጥንታዊ የሆኑ ሁለቱ አገራት፣ ኢትዮጵያና ግብፅ ለዘመናት የሰው ዘር ታሪክ፣ ቅርስና ታላቅ ሥልጣኔ አሻራ ማሳያ የሆኑ ታላላቅ አገራት መሆናቸው በሰፊው ሲጠቀስ ቆይቷል፣ አሁንም ይጠቀሳሉ፡፡

ለእነዚህ አገራት ታሪክ፣ ታላቅ ሥልጣኔና ዕድገት መነሻና እምብርት ደግሞ የዓባይ ወንዝ እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ይጠቁማሉ፡፡ ታላቁ ቅዱስ መጽሐፍም፡- ‹‹ስለ ዔደን ገነት ሲያትት የዔደን ገነትን ከከበቡትና ከሚያጠጡት ወንዞች መካከል አንዱ የዓባይ ወይም የግዮን ወንዝ መሆኑን በግልጽ አስቀምጦታል፡፡ የዘፍጥረት ጸሐፊ የሆነው እስራኤላዊው ነቢይ ሙሴ ይኽው የዓባይ ወንዝም ኢትዮጵያን መሬት ሁሉ እንደሚከብ ይናገራል፡፡››

በክርስቲያኖች ቅዱስ መጽሐፍ ዘንድም ሆነ በእስልምና ሃይማኖት ቅዱሳን መጻሕፍት የከበረ ስምና ዝና ያላት ኢትዮጵያ ገና ከፍጥረት ማግሥት ጀምሮ የራሷን መንግስት አቋቁማ የምትኖር፣ ኃያላ፣ ባለ ታሪክና ልዑላዊት አገር እንደነበረች ይመሰክራሉ፡፡ በተጨማሪም ኢትዮጵያ የዓለማችን ታላቅ የሆኑ የአይሁድ፣ የክርስትና እና የእስልምና ሃይማኖቶች ማእከል እንደሆነችም ይታወቃል፡፡

ኢትዮጵያ የታሪክ፣ የሃይማኖትና የሥልጣኔ ማእከል መሆኗ ብቻ ሣይሆን ከኢትዮጵያ ምድር ፈልቆ ሱዳንና ግብፅን አቋርጦ ወደ ሜድትራኒያን ባሕር የሚገባው የዓባይ ወንዝ አያሌ ዘመናትን ላስቆጠረው ለግብፃውያኑ አፍሪካዊው ሥልጣኔ፣ መነሻና መሠረት እንደነበር የታሪክና የአንትሮፖሎጂ ምሁራን አስረግጠው ጽፈዋል፡፡

ከእነዚህም ምሁራን መካከል አፍሪካውያኑ ስመ ጥር፣ እውቅ ምሁራንና የታሪክ ተመራማሪዎች የሆኑት ሼክ አንታዲዮፕና ኢቫን ኢቫን ሰርቲማ በጥናታቸው፡- ‹‹ግብፅ የኢትዮጵያ ሥልጣኔ የመንፈስ ልጅ›› እንደሆነች ባሳተሙት በዳጎስ ጥናታቸው በግልጽ ጽፈዋል፡፡

ኢትዮጵያንና ግብፅን ከሚያስተሳስሩ ዋና ጉዳዮች በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው ታሪካዊው የዓባይ ወንዝ ነው፡፡ ዛሬ ዓለም ጉድ የሚሰኝበት የግብፃውያኑ ታሪክ፣ ቅርስና ታላቅ ሥልጣኔ መሠረቱ የዓባይ ወንዝ ነው፡፡ እነዛ ዓለምን ጉድ ያሰኙና በየቀኑ በብዙ ሺህ የሚቆጠር ቱሪስቶችን ቀልብና ዓይን የሚቆጣጠሩ የግብፅ ፒራሚዶች የተገነቡት የዓባይ ወንዝ ዳርቻን ተከትለው ነው፡፡

ግብፅና ግብፃውያን ከዓባይ ውጪ የሚኖሩት ሕይወት፣ የሚተርኩት ታሪክ፣ ዓለም ሁሉ የሚያየው፣ የሚያደነቅውና ጉድ ጉድ የሚሉለት አንዳንችም ሥልጣኔም ሆነ ቅርስ የላቸውም፡፡ ዓባይ ለግብፅና ለግብፃውያን ሁሉን በሁሉ ነው ብንል ብዙም ከእውነታው የራቅን አይመስለኝም፡፡ ለዚህም ይመስለኛል በተለምዶ ‹‹ታሪክ አባት›› ተብሎ የሚጠራው ጥንታዊው ታሪክ ጸሐፊ ግሪካዊው ሄሮዱተስ Egypt is the gift of Nile ሲል በአጭር ቃል ግብፅን የገለጻት፡፡

እናም ኢትዮጵያና ግብፅ ለዘመናት ተሳሰረው የቆዩበት እትብት የዓባይ ወንዝ መሆኑን ማንኛችንም ብንሆን እንስተዋለን ብዬ አልገምትም፡፡ ይህ በዓባይ ወንዝ አማካኝነት የተፈጠው የሁለቱ አገራት ታሪካዊ ትስስር የክርስትና ሃይማኖት ወደ ኢትዮጵያ መግባት በኋላ ደግሞ ሌላ የሃይማኖትና የታሪክ የቃል ኪዳን ውልን ፈጠረ፡፡ ከ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በኋላ የኢትዮጵያ የስልጣኔ ልጅ ናት ተብላ የተጠቀሰችው ግብፅ ዳግም ለኢትዮጵያውያን የመንፈስ እናት ሆና በታሪክ መድረክ ብቅ አለች፡፡

ይህ ግብፃውያን በሃይማኖት ስም ከኢትዮጵያ ጋር የተሳሰሩበት የእናትነትና የልጅነት መንፈስ የፈጠረውን ወይም ያመጣውን መንፈሳዊ ፋይዳና ጥቅም፣ እንዲሁም ያሰከተለውን መንፈሳዊና አሥተዳደራዊ ቀውስና ውጥንቅጥ ለመተንተን የዚህ ጽሑፍ ዓላማ አይደለም፡፡ ይሁን እንጂ እዚህ ጋር ሳይነሳ ሊታለፍ የማይገባው ነጥብ ቢኖር፡- ግብፃውያን በሃይማኖት ስም በኢትዮጵያ ላይ የጫኑት ከባድ ቀንበርና ብርቱ ክንድ ከጊዜ በኋላ መልኩን ቀይሮ ወደ ፍፁም አምባገናነዊነትና ቅኝ ግዛትነት ተቀይሮ እንደነበር ሁላችንም ቢሆን ልንዘነጋው አይገባንም፡፡

በወርቅ፣ በእንቁ፣ በከበሩ ስጦታዎች ጋጋታ ወደ ኢትዮጵያ ይመጡ የነበሩት በጣት ከሚቆጠሩት ግብፃውያን ጳጳሳት በስተቀር የሚበዙት ከስምና ከምልክትነት ባለፈ (Puppet Fathers) ይሄ ነው የሚባል ሥራ እንዳልነበራቸው የቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ አጥኚዎች በግልጽ ይናገራሉ፡፡

በተለይም ደግሞ ግብፅ ሙሉ በሙሉ በሙስሊም ወራሪዎች እጅ ከወደቀችበት ዘመን ጀምሮ ግብፃውያኑ ገዢዎች በጳጳሳቱ በኩል ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ የሆነ አጀንዳቸውን ለማስፈጸም በተቀነባበረና በረቀቀ ሴራ እንዲያም ሲል በኋላኛው ዘመን በጦር ኃይል አጀንዳቸውን ለማስፈጸም ወደኋላ እንዳላሉ የታሪክ ድርሳናቶቻችን በሚገባ ያስረዳሉ፡፡

ግብፃውያኑ ኢትዮጵያ አንድ ቀን የዓባይን ወንዝ ልትገድብ ትችላለች የሚለው ስጋታቸው ቀን ከሌሊት እረፍት ስለማይሰጣቸው ዓባይን በዓይነ ቁራኛ ነበር የሚከታተሉት፡፡ እናም ኢትዮጵውያኑ በዓባይ ወንዝ ላይ ያላቸውን ማንኛውንም እንቅስቃሴ ይቃኙ ዘንድ ሁለት ሼኼዎችን ጳጳስ አድርገው በተለያዩት ጊዜያት በቃፊርነት ወደ ኢትዮጵያ ምድር ልከው እንደነበር የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊዎች ይህን የግብፃውያኑን አሣፋሪ ቅሌት በታሪክ ድርሳናት ውስጥ አስፍረውታል፡፡

በኢትዮጵያ በኩልም የዓባይ ወንዝ ለአናሳዎቹ ግብፃውያን ክርስቲያኖች የመደረደሪያና ለግብፃውያኑ ገዢዎች ማስፈራሪያ መሣሪያም በመሆን ያገለገለበት በርካታ ጊዜያቶች ነበሩ፤ በተለይም ደግሞ በዛግዌ ስርወ መንግሥትና በመካከለኛው ዘመን ታሪካችን፡፡

በእነዚህ ሁለት ጥንታዊ እና የታላቅ ሥልጣኔ ባለቤቶች በሆኑ ሀገራት መካከል በየጊዜው ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ይነሳ የነበረው የዓባይ ውኃ ጉዳይ ነበር፡፡ እናም በዛግዌ እና በመካከለኛው የኢትዮጵያ የታሪክ ዘመን ወደ ግብፅ የሚፈሰው የዓባይ ውኃ መጠን በቀነሰ ቁጥር ጉዳዩ አሳሳቢ እየሆነ መነሳቱን ከታሪካችን እንረዳለን፡፡

የግብፅ ነገሥታት አልፎ አልፎ የዓባይ ወንዝ በምንጩ አካባቢ በሚደርስ ድርቅ ምክንያት የፍሳሹ መጠን የሚቀንስ መሆኑን ባለመጠርጠር፣ የኢትዮጵያውያን ውኃን የዘጉት ወይም ወደ ሌላ አቅጣጫ እንዲፈስ ያደረጉት እየመሰላቸው፣ ውኃውን ለማስለቀቅ ወደ ኢትዮጵያ ነገሥታት ዘንድ በየጊዜው መልእክተኛ ይልኩ ነበር፡፡

ለምሳሌ ታሪክ ጸሐፊው የዓረብ ተወላጅ አል ማኪን ድርጊቱ ከሆነበት ከሁለት መቶ ዓመት በኋላ ሲጽፍ በፋቲሚድ ሥርወ መንግሥት በሡልጣን አቡ ታምሊን አል ሙስታንዚር የአገዛዝ ዘመን (1036-1094) ግብፅ የሚደርሰው የውኃ ብዛት በ1089-1090 አካባቢ ቀነሰ፡፡ በዚህ የተነሳ ሡልጣኑ ወዲያውኑ የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ አባ ሚካኤልን ከፍ ያለ ገጸ በረከት አስይዞ ኢትዮጵያውያን የተቋረጠውን የዓባይን ወንዝ እንዲለቁ ለመለመን ወደ ኢትዮጵያ እንደላካቸው አትቷል፡፡

አል ማኪን ጉዞውም በ1092 እና በ1094 ዓ.ም ማሃል ባለው ጊዜ ውስጥ ነበር በማለት፤ የኢትዮጵያዊው ንጉሠ ነገሥት የነበረው ይምርሃነ ክርስቶስ አንድ ኮረብታ እንዲፈርስ ባዘዘ ጊዜ የውኃው መጠን በአንድ ሌሊት ሦስት ጫማ ከፍ ብሎ አደረ ሲል በመጽሐፉ በሰፊው ተርኮአል፡፡

14ኛው መቶ ክ/ዘመን የግብፅ ማምሉክ ሡልጣን አል ናሲር ሙሀመድ ኢብን ቃላኡን በርካታ አብያተ ክርስቲያናት የማፍረሱና ክርስቲያን የሆኑ ዜጎቹን በጽኑ የማሰቃየቱ ዜና ወደ ኢትዮጵያ ደርሶ ከፍ ያለ የኀዘን ስሜት መፍጠሩን አል ማቅሪዝ የተባለው የሞሮኮ ተወላጅ ታሪክ ጸሐፊ በወቅቱ ዘግቦአል፡፡

በታሪኩ ውስጥ ስሙ ባይጠቀስም ከ1380-1409 ዓ.ም የነገሠው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት አፄ ዳዊት አንድ የልዑካን ቡድን ወደ ግብፅ ልኮ የዓባይን ወንዝ ፍሳሽ ወደ ሌላ አቅጣጫ በማዞር የግብፅን ሕዝብ በራብ ለመፍጀት እንደሚችል ለግብፁ መሪ በብርቱ ማስጠንቀቂያ ገልፆለት እንደነበር ጽፎአል፡፡

ኢብን ፋድል አል አልዑማሪ የተባለ አንድ የግብፅ ቤተ መንግሥት ባለሟልና ጸሐፊ ‹‹ማሳሊክ አል አብሳር ፊ ማምሊክ አል አምሳር›› ቀጥታ ትርጉሙ ‹‹የነገሥታት ምድር ቅኝት›› በሚል ርዕስ በዘመኑ ያስተዋለውን የተለያየ ነገር ጽፎ ነበር፡፡ በዚህ መጽሐፉ ሀበሾች (ኢትዮጵያውያን) ወደ ግብፅ የሚፈሰውን ዓባይን እንደሚቆጣጠሩና ለግብፅ ሡልጣን ከበሬታ ሲሉ ብቻ ውኃው እንደተለመደው ወደዚያ እንዲፈስ የሚፈቅዱ መሆናቸውን ይናገራሉ ሲልም ገልጾአል፡፡

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ከግብፃውያኑ መንፈሳዊ ባርነትና ፖለቲካዊ ሴራ ትላቀቅ ዘንድ የኢትዮጵ መንፈሳዊ አባቶችና ንጉሡ ቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ባደረጉት ያላሰለሰ ጥረት ቤተ ክርስቲያኒቱ ከ1600 ዓመታት መራር የግብፃውያን ቀንበር ተላቃ የራሷን መንፈሳዊ መሪ ካገኘች አምሳ ዓመታት ያህል ተቆጥረዋል፡፡ ምንም እንኳን ቤተ ክርስቲያኒቱ ከግብፃውያን አገዛዝ ብትላቀቅም ሁለቱን አገራትን በሚያስተሳስራቸው በዓባይ ጉዳይ ላይ አሁንም ድረስ ግብፃውያኑ ክርትስቲያኖች ሆኑ ሙስሊሞች ያላቸው አቋም በዓባይ ላይ ለምን ሲባል ጥያቄ ታነሳላችሁ የሚል ዓይነት ጠንካራና ግትር ነው፡፡

ግብፃውያኑ ኢትዮጵያ በዓባይ ላይ ያላትን የመጠቀም መብት በተመለከተ ሲነሳ ሁሌም ዓይናቸው ደም ነው የሚለብሰው፣ ይህ ቅናታቸውና ቅንነት የጎደለው ጭፍንነታቸው ከዓባይ አልፎም ኢየሩሳሌም ድረስ ሣይቀር እንኳን ተሻግሮ በኢትዮጵያውኑ ጥንታዊ ይዞታ በሆነው በዴር ሱልጣን ገዳም ላይ ያሳረፈውን ብርቱ ጥላቻና ክንድ አይተናል፣ ታዝበናልም፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ምናልባት በሌላ ጊዜ ሰፋ አድርጌ እጽፍ ይሆናል፡፡

ግብፃውያኑ እንቀድሞው ዘመን በመንፈሳዊነት ስም ኢትዮጵያንም ሆነ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን ዳግም በቅኝ ገዢነት መንፈስ ይዘው ዓላማቸውን ለማስፈጸም ምንም ዓይነት ዕድል እንደሌላቸው ካወቁ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ የዓባይ ውኃን በተመለከተ ኢትዮጵያ ፍትሐዊ በሆነ መንገድ የመጠቀም መብቷ ሙሉ በሙሉ የተጠበቀ እንደሆነ ግብፅና ግብፃውያን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተረዱት መጥተዋል፡፡ እንደቀደመው ዘመን በማስፈራራትና በዲፕሎማሲያዊ ጫና የዓባይን ውኃ ከመጠቀም የሚከለክሉበት ምክንያት እንደሌላቸውም እርግጥ ሆኗል፡፡

አሁን አሁን ከግብጽ እየወጡ ያሉ መረጃዎችና ዜናዎች እንደሚያሳዩትና በቅርቡ ፕሬዝዳንት ሙርሲም እንዳረጋገጡት፡- ‹‹ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ የምታካሂደው ልማት ግብፅንና የተቀሩት የተፋሰሱን አገሮች እስካልጎዳ ድረስ ደስተኞች ነን፡፡ ከጎናችሁም እንቆማለን ሲሉ እየተደመጡ ነው፡፡›› ይህ ከልብና ከቅንነት የመነጨ ከሆነ መልካም የሚባል እርምጃ እንደሆነም የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብም እየገለጹ ናቸው፡፡

ሕዝባችን ለዘመናት ከተጣበው ድህነት፣ የመከራ፣ ሰቆቃና የስደት ሕይወት ተላቆ በአገሩና በሕዝቡ መካከል ተረጋግቶና እፎይ ብሎ መኖር እንዲችል ሰላም፣ ዲሞክራሲ፣ ፍትሕ፣ መልካም አስተዳር፣ ልማት … ወዘተ በጣሙን አስፈላጊ ናቸው፡፡

መንፈሳዊ ተቋማትና መሪዎቻቸው በአገራችን ሰላም፣ ዲሞክራሲ፣ ፍትሕ፣ መልካም አስተዳደር፣ ዕድገትና ብልጽግና እንዲሰፍን የራሳቸው የሆነ ከፍተኛ ድርሻና ተሣትፎ አላቸው፡፡ በቅርቡም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መሪ የሆኑት ፓትርያርክ አቡነ ማቲያስ በዓባይ ወንዝ ላይ ስለተጀመረው ልማት፣ በዴር ሱልጣን ገዳማት ጉዳይና እንዲሁም በቤተ ክርስቲያኒቱ የተንሰራፋውን ሙሰናና ሙሰኞችን በተመለከተ ያስተላለፉት መልእክት ብዙዎችን ደስ አሰኝቷል፡፡

የቅዱስነታቸው ይህ ቃል ከቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት ብፁዓን አባቶቻች ጋር በመተባበር ተግባራዊ ሆኖ የምናይበትን ጊዜ መንፈሳዊ ልጆቻቸው በታላቅ ጉጉት እንጠብቃለን፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስለተንሰራፋው ሙስና፣ የመልካም አስተዳደር እጦት፣ የሞራል ዝቅጠትና ውድቀት፣ እንዲሁም የመንፈሳዊነት ሕይወት መታጣት ብዙ የተባለለት ያረጀና ያፈጀ ጉዳይ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ችግሩን ከማውራት በስተቀር ይህን ነው ተብሎ ሊነሣ የሚችል ተግባራዊ እርምጃ እስካሁን አልተወሰደም፡፡

እንዲሁም ቅዱስ ፓትርያርኩ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ያጣበቡትን ነጋዴዎችና ዘራፊዎች ያለ ምንም ቅደም ሁኔታ በማስወጣት መንፈሳዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰዱና፣ በተጨማሪም የተሠጣቸውን መንፈሳዊ የሆነ ኃላፊነት ዘንግተው ፍጹም መንፈሳዊ ባልሆነ አካሄድ በሥጋዊና በዓለማዊ ምኞት ተጠልፈው፣ ያልደከሙበትንና ያለፉበትን ሀብትና ገንዘብ የማከማቸት ሥራ ውስጥ ተዘፈቁ የቤተ ክርስቲያኒቱን ኃላፊዎች ተገቢውን ሥርዓት እንዲይዙ እንደሚያደርጉ ያስተላለፉት መልእክት በእውነት ይበል የሚያሰኝ ነው፡፡

ቅዱስ ፓትርያርኩ በመንፈሳዊ ቅንአትና ቆራጥነትና እንዲሁም ባላቸው ከፍተኛ መንፈሳዊ ኃላፊነትና እረኝነት በቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ አገልጋዮችና ተከታዮቿ መካከል ለአገርና ለወገን የሚቆረቆር፣ የተሠጠውን ግዴታውንና ኃላፊነቱን በታማኝነት የሚወጣ፣ በወንጌል የእውነት ቃል የታነጸ መልካም ዜጋና ትውልድ ለመፍጠር ከቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ አባቶች ጋር የበኩላቸውን ጥረት በማድረግ ተወዳጅና ተከባሪ አባት እንዲሆኑልን እመኝላችኋለሁ፡፡

በተጨማሪም ቅዱስ ፓትርያርኩ የዓባይን ውኃ በፍትሐዊነት የመጠቀም መብታችንን በተመለከተ ቤተ ክርስቲያኒቱ ከግብፅ ጋር የነበራትንና አሁንም ያላትን የረጅም ዘመን ግንኙነትና እንዲሁም ታሪካዊ ትስስር ከግምት ውስጥ በማስገባት የጀመሩትን እንቅስቃሴ ይቀጥሉበታል የሚል ጽኑ ተስፋ አለኝ፡፡

ከግብፃውያን ጋር ለረጅም ጊዜያት አተካራ በገባንበትም በዴር ሱልጣን ገዳማችን ጉዳይን በተመለከተም ፓትርያርኩ በኢየሩሳሌም ለረጅም ዓመታት በመቆየታቸው ያለውን ሃይማኖታዊ ሆነ ፖለቲካዊ ችግሩን በሚገባ ያውቁታልና ቅዱስ ሲኖዶስንና መንፈሳዊ ልጆቻቸውን በማስተባበር ሰፊ የሆነ ሥራን ሊሠሩ እንደሚችሉ መንፈሳዊ ልጆቻቸው ተስፋ እናደርጋለን፡፡

በቀጣይ ጽሑፌ በዴር ሱልጣን ገዳም ዙሪያ ያለውን ታሪክና የግብፃውያኑን ሴራ ከወቅታዊው የዴር ሱልጣን ገዳም ጉዳይ ጋር አያይዤ ለመጻፍ ከወዲሁ ቃል በመግባት ልሰናበት፡፡

ሰላም! ሻሎም!

ቃለምልልስ የሶማሊያውን ክልል ፕሬዚዳንት ምስጢራዊ ቪድዮዎችን ለአደባባይ ካበቃው አብዱላሂ ሁሴን ጋር

“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም የመሬት ነጠቃ፤ በኢትዮጵያ” ጥናት ትርጉም ይፋ ሆነ (ሊያነቡት የሚገባ)

$
0
0

cover 6
ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን)
ግንቦት 5፣ 2005ዓም

በኢንቨስትመንት ስም የአገር ሃብትና ትውልድን እየበላ ስላለው የመሬት ነጠቃ አስመልክቶ የኦክላንድ ተቋምና ድርጅታችን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በጋራ ያዘጋጁት ጥናታዊ ዘገባ ይፋ ሆነ። የጋራ ንቅናቄያችን ዋና ዳይሬክተር ጥናቱ በትክክለኛ ጭብጥ ላይ ተመስርቶ እንዲዘጋጅ ለህይወታቸው ሳይሳሱ መረጃ በመስጠት ለተባበሩ ዜጎች “ታላቅ ክብር ይሁንላችሁ። አሁን አትታወቁም። ግን ከቶውንም አትረሱም። ክብር ለማትታወቁት ግን ለማትረሱት የአገር ጀግኖች” በማለት ምስጋና አቅርበዋል።
ኢህአዴግን በደፈናው መቃወምን ዓላማው ያላደረገው ይህ ጥናታዊ ዘገባ ዜጎችን ካደጉበት፣ ከኖሩበት፣ ከቀያቸው፣ ከህልውናቸው፣ ከርስታቸው፣ ወዘተ ያለ አንዳች ውይይት፣ ምክክርና ንግግር በማፈናቀል ለውጪ ኩባንያዎችና ለራሱ ለባለጠመንጃው አገዛዝ ሰዎችና ባለሟሎች መሬት ማከፋፈሉን በማስረጃ ያሳያል። የራሱ የኢህአዴግ አካላትም በሪፖርቱ ውስጥ በአግባቡ ድምጻቸው ተካትቷል። የሚጠቀሙባቸው አዋጆችና ህጎችም አልተዘለሉም።
“የውጪ ባለሃብቶችና ኩባንያዎች ወደ አገር ውስጥ መግባታቸው ለቴክኖሎጂ ዝውውር፣ በአገሪቱ ያለውን የምግብ እጥረት ለማስወገድ ይረዳል” የሚሉ ምክንያቶች እያቀረበ ያለው ኢህአዴግ በተግባር ሲፈተሽ ተግባሩና ዓላማው ምን እንደሆነ የሚያመለክተው ጥናቱ የስርዓቱ ሰለባዎች፣ የኢህአዴግ ባለስልጣናት፣ ኢንቨስተሮች፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ክፍሎች፣ የቅርብ ምስክሮች፣ የተለያዩ ከዓለምአቀፍ ተቋማት የተገኙ መረጃዎች፣ አገዛዙ ራሱ ይፋ ያደረጋቸው መረጃዎችና ለጥናቱ አስፈላጊ የተባሉ አኻዞች የተካተቱበት በመሆኑ እውነታውን ህዝብና ማናቸውም ወገኖች እውነቱን ለመረዳት ያስችላቸዋል ተብሎ በጉልህ ታምኖበታል።
በምሳሌ ለማሳያነት የተጠቀሰው የሳዑዲ ስታር ኩባንያ የሚያመርተውን ሩዝ ደብረዘይት በገነባው ተቋሙ አማካይነት ሩዙን የመለየትና ለኤክስፖርት የማዘጋጀት ስራ ይሰራል። የተመረጠውና መለኪያውን የሚያሟላው ሩዝ ኤክስፖርት የሚደረግ ሲሆን፣ ደቃቃውና በሚሊሜትር ተለክቶ ለኤክስፖርት ደረጃ የማይበቃው አገር ቤት እንዲቀር ይደረጋል። ከዚህ አንጻር እንኳ ቢታይ የመሬት ኢንቨስትመንት የተባለው ዓለም ጠንቅቆ ለሚያውቀው የአገራችን የምግብ እጥረት ችግር መፍትሄ ሊሆን አይችልም። በጥናቱ ዝርዝር ጉዳዩ አለ።
ኢህአዴግ በፖለቲካው ውድማ ላይ ቆሞ የሚያወራውና በተግባር የሚሆነውን እውነት ከሰለባዎቹ አንደበት በመቅዳት ሊስተባበል በማይችልበት ደረጃ ያቀረበው ጥናት፣ ዜጎች ከቀያቸው ከመፈናቀላቸው በፊት ምክክርና የስነልቦና ዘግጅት እንዲደረግ ጊዜ እንደሚሰጥ በህግ የተደነገገ ስለመሆኑ፣ ነግር ግን እውነታው የተገላቢጦሽ መሆኑንን ጥናቱ በማስረጃ ያትታል። ዜጎች ነገ ስለሚሆነው እንኳ ሊያውቁ በማይችሉበት ደረጃ ማለዳ ካረፉበት ሲነቁ ዶዘር ማሳቸውን፣ የጓሮ አትክልታቸውን፣ የኑሯቸው መሰረት የሆነውን ደናቸውን፣ ቤታቸውን ሲጠርግ እንደሚያዩ እነዚሁ መከረኞች ለህይወታቸው ሳይሳሱ መናገራቸውን ጥናቱ ትኩረት ሰጥቶ አቅርቦታል።
የመሬት ካሳ እንኳ ባግባቡ የማያገኙት ወገኖች በራሳቸው አንደበት፣ በግብር የደረሰባቸውንና ከፊት ለፊታቸው ያለውን አደጋ አስመልክቶ በዝርዝር ሚዛናዊ በማድረግ ያቀረበው ጥናት ኢህአዴግ ለማስተባበል ከፈለገ በዜናና በተራ ጩኸት ሳይሆን በመረጃ የተደገፈ፣ ሁሉንም ወገኖች ያካተተ ሚዛናዊ ሪፖርት ካቀረበ ብቻ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) በማስተባበያነት እንደሚቀበለው አስቀድሞ ለመግለጽ ይወዳል።
በአገርና በግለሰብ ደረጃ መረጃ ለማዳረስ፣ በተመሳሳይ ኢህአዴግ የሚያሰራጨውን የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ማጋለጥ፣ የሰብአዊ መብት ጥሰቱን ማሳየት፣ የተሳሳተውን ፖሊሲ ማስቀየር ዋናው የጥናቱ ዓላማ ነው። በጥናቱ በቀረበው ጭብጥ መሰረት የዓለም ባንክ፣ ወዳጅ አገሮች፣ አበዳሪ አገሮች ፖሊሲ አውጪዎች ወዘተ አካሄዳቸውን እንዲመረምሩ ለማስቻል ሰፊ ስራ የተሰራ መሆኑንን በዚህ አጋጣሚ እንጠቁማለን። በተለያዩ አጋጣሚዎች የተለያዩ የውጪና የአገር ውስጥ ሚዲያዎች እንደዘገቡት ሰፊ ስራ የተሰራ ቢሆንም፣ በዋናነት የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ምን እየተሰራ እንደሆነ ሲረዳ ትግሉን ማቅለል፤ ውጤቱንም ማቅረብ ይቻላል የሚል እምነት አለን።
በዚህና በሌሎችም ተዛማጅ ምክንያቶች በከፍተኛ የሃላፊነት ስሜት፣ ረዥም ጊዜ ተወስዶ የተሰራው የትርጉም ሰራ ሰውን የሚያክል ክቡር ፍጥረት ከማደሪያው እንዲወጣ ተደርጎ እንዴት ወደ ጉድጓድ እንደሚወረወር ለመጪው ትውልድ በታሪክነት፣ አሁን ላለነው በመረጃነት፣ ከሁሉም በላይ ከጩኸትና ከመረጃ አልባ ክስ የምናገኘው ጥቅም አለመኖሩን በመረዳት አቋቋምን ለማስተካከል ይረዳል፣ ታላቅ ምሳሌም ይሆናል ብለን እናምናለን።
ጥናቱን በማሰራጨትና ዜጎች እጅ እንዲደርስ በማድረጉ በኩል የሁሉም ወገኖች ያልተቆጠበ ጥረት እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ ለመግለጽ እንወዳለን። በዚህ አጋጣሚ እናወጣዋለን ብለን ካሰብንበት ጊዜ በማለፍ ተጨማሪ ሳምንታት በማዘግየታችን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡ በአገራችን ካለው የመረጃ አፈና አኳያ የጥናቱ መጠን ሰብሰብና አጠር ባለ መጠን በኢሜይል እንደሚሰራጭ ሆኖ በአዲስ መልክ ሲቀናበር ተጨማሪ ሳምንታትን መውሰዱ የግድ ሆኗል፡፡
የጋራ ንቅናቄያችን ጽሁፉን የማሰራጨቱ ስራ በጨዋነት፣ ለጽሁፉ ባለቤቶች (ለእንግሊዝኛው የኦክላንድ ተቋም ለአማርኛው ደግሞ አኢጋን) አስፈላጊውን እውቅና በመስጠት እንዲሆን በዚህ አጋጣሚ አበክረን እንሳስባለን። ከመሬት ነጠቃ በላይ የከፋ ወንጀል የለም። ዜጎችን በምድራቸው ወደ ባርነት የሚያሸጋግረው የመሬት ነጠቃ የአገሪቱን ሃብትና ንብረት እየበላ ነው። ይህንን ወደር የሌለው ወንጀል ለማጋለጥ፣ ለመታገል፣ ለመቃወምም ሆነ ተዛማጅነት ያላቸው ተግባራት ለማከናወን ለሚፈልጉ ተቋማት፣ ግለሰቦችና ሚዲያዎች ይረዳ ዘንድ (Land Grab – http://landgrabsmne.wordpress.com) የሚባል ብሎግ እንዲሁም በፌስቡክ Land Grab/መሬት ነጠቃ መከፈቱን ለማሳወቅ እንወዳለን። በቅርቡ የሚሻሻለው ይህ ብሎግና የፌስቡክ ገጽ ከመሬት ወረራ ጋር በተያያዘ ሁሉም ዓይነት ማስረጃዎች የሚታተሙበት ስለሚሆን መረጃ ለሚፈልጉ ወገኖች ሁሉ መልካም አጋጣሚ ይሆናል።

Download (PDF, 1.93MB)


በኢሜይል ለማግኘት የሚፈልጉ በሙሉ በሚከተለው አድራሻ (media@solidaritymovement.org) ቢጠይቁን በቀጥታ የምንልክ መሆናችንን እናሳውቃለን፡፡
በመጨረሻም የጋራ ንቅናቄያችን ዋና ዳይሬክተር ለተርጓሚው ከሁሉም በላይ ግን የስርዓቱ ላንቃ ስር ሆነው የህይወት ዋጋ በመክፈል መረጃ ለሰጡት ወገኖች የአክብሮት ምስጋና አቅርበዋል። አቶ ኦባንግ በመልዕክታቸው “በቦታው ላይ ሆናችሁ ለህይወታችሁ ሳትፈሩ ይህንን መረጃ የሰጣችሁ ሁሉ የአገር ጀግኖች ናችሁ፤ አሁን አትታወቁም። አሁን ልንገልጻችሁ አንችልም። ጊዜና ወቅት ጀግንነታችሁን እስኪገልጹት ግን አትረሱም። ልትረሱም አትችሉም። ብዙ ባይነገርላችሁና ባይዘመርላችሁም ታላቅ ስራ ሰርታችሁዋልና ክብር ይሁንላችሁ” ብለዋል፡፡
ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ
የሚዲያና ሕዝብ ግንኙነት ግብረኃይል
*********************************************************************************************************
ለዚህ ደብዳቤ ምላሽም ሆነ ለተጨማሪ መረጃ ዋና ዳይሬክተሩን ለሚዲያ ክፍሉ (media@solidaritymovement.org) በመጻፍ ወይም ድረገጻችንን (www.solidaritymovement.org) በመጎብኘት ለመረዳት ይችላሉ፡፡

Download (PDF, 1.93MB)

“በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም የመሬት ነጠቃ፤ በኢትዮጵያ” ጥናት ትርጉም (117 ገጾች –ጥብቅ ምስጢር)

ከሙስናው በስተጀርባ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

$
0
0

ከኢየሩሳሌም አርአያ

tplf-rotten-apple-245x300በሕወሐት የተፈጠረው የቀውስ ማእበል አድማሱን እየለጠጠ መሔዱን ተከትሎ «ታማኝ» ሆነው በሙስና ሲያገለግሉ የቆዩትን ጭምር እየበላ እንደሚገኝ የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። በቀዳሚነት የሚያነሱት በጉምሩክ ቁልፍ ስልጣን የነበረውን የሕወሐት አባል ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ሲሆን እንዴትና በማን ወደስልጣን እንደመጣ እንዲሁም ምን-ምን ተግባራት ይፈፅምና ያስፈፅም እንደነበረ ምንጮቹ ሂደቱን እንደሚከተለው ይገልፁታል።

ገ/ዋህድ በ1993ዓ.ም ፓርቲው ለሁለት መሰንጠቁን ተከትሎ ወደ ስልጣን እንዲመጣ ተደረገ። ከጉምሩክ ሃላፊነት በተጨማሪ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተርነት ስልጣን እንዲጨብጥ የተደረገው በአቶ መለስ በተለይ በአዜብ ይሁንታ ጭምር እንደነበረ ምንጮቹ ይጠቁማሉ። ገ/ዋህድ ለዚህ ስልጣን የበቃው ለአቶ መለስ ቡድን በከፈለው መስዋእትነት ሲሆን በክፍፍሉ ማግስት የሙስና ዘመቻ ተከፍቶ እነአባተ ኪሾና ሌሎች እስር ቤት እንዲገቡ ቀጥተኛ ትእዛዝ ከመስጠት አንስቶ ራሱ ክስ አዘጋጅ፣ምስክርና ፈራጅ..በመሆን የላቀ ሚና መጫወቱን ያስታውሳሉ። በዚህ ተግባሩ የበለጠ ታማኝነቱን በማሳየቱ ከአዜብ በሚሰጠው ቀጥታ ትእዛዝ ሙስናውን ማከናወን መቀጠሉን ምንጮቹ አያያዘው ይጠቁማሉ። በ10ሺህ ቶን የሚገመት ቡና ከአዜብ በተቀበለው ትእዛዝ በህገወጥ መንገድ ከአገር ተዘርፎ የተሸጠበትና ጉዳዩም በፓርላማ ተነስቶ በጠ/ሚ/ሩ «የሌቦቹን እጅ እንቆርጣለን» የሚል አስቂኝ ምላሽ መሰጠቱን ያስታውሳሉ። በተጨማሪ በጉምሩክ ለረጅም አመት በመምሪያ ሃላፊነት ሽፋን የተቀመጠውና የቢሮውን የበላይ ሃላፊዎች በጥብቅ ከመቆጣጠር ጀምሮ እያንዳንዱን የሙስና ተግባር ከጀርባ ሆኖ የሚያስፈፅመው የአዜብ የቅርብ ስጋ ዘመድ ፍትሃነገስት ክንደያ እንደሚጠቀስና ግለሰቡ ቀረጥ ያልተከፈለባቸው 500 ሳተላይት ዲሾች እንዲገቡና በአዜብ በበላይነት ይመራ ለነበረው የዘረፋ ቡድን ለሰባት አመታት በየወሩ 20ሚሊዮን ከቴሌ በህገወጥ መንገድ እንዲዘረፍ ያደረገና በኋላም ከነገ/ዋህድ ጋር ሆኖ በርካታ ሙስናዎችን በዋናነት በማስፈፀም እንደሚጠቀስ ያመለክታሉ።

በሌላም በኩል የገ/ዋህድ ባለቤት ኰ/ል ሃይማኖት ስትጠቀስ ከሕወሐት አንጋፋ ሴት ታጋዮች አንዷ ናት፤ ከጡረታ ጋር በተያያዘ ከመከላከያ በመልቀቅ በአዜብ የበላይነት በሚመራው የሴቶች እና ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ቢሮ መስራት ቀጠለች። ለዚህ ቢሮ ከአሜሪካ መንግስት ብቻ በአመት እስከ 240ሚሊዮን ዶላር ይለገሳል። ገንዘቡ ለሚመለከታቸው ወገኖች ሳይሆን የሚውለው የነአዜብ ኪስ ማደለቢያ ሆኖ እንደሚዘረፍ ያመለከቱት ምንጮች ይህም ጉዳይ በፓርላማ ለቀድሞ ጠ/ሚ/ር ተነስቶ « ከእንግዲህ ቁጥጥር እናደርጋለን» የሚል የተድበሰበሰ ምላሽ እንድተሰጠ ያስታውሳሉ። ባልና ሚስቱን በተለያየ ወጥመድ በማስገባት የሙስና ጋሻ-ጃግሬ አድርገው የቆዩት አዜብ እንዲሁም ሌሎቹ ቱባ ባለስልጣናት መጠነ-ሰፊ ዘረፋና ሙስና ጉዳይ ሳይነካ ግልገሎቹን ብቻ (ያውም በአስፈፃሚነት ራሳቸው የመደቧቸውን) ተጠያቂ ማድረግ ተራ ድራማ ነው ሲሉ ምንጮቹ ያጣጥሉታል። በማስረጃነትም፥ 400 ሚሊዮን ብር ለ«ራዲሰን ሆቴል ግንባታ» በሚል ሽፋን በመፍቀድ 150ሚሊዮን ኪሳቸው ከከተቱትና በርካታ ብድሮችን በመፍቀድ (የስጋ ዘመዶቻቸውን ደላላ በማድረግ…) በሙስና የደለቡት አባይ ፀሃዬ ጨምሮ፣ የበታች ሙሰኞች ላይ <ምስክር> ሆነው የቀረቡትና ከአዜብ ጋር በሙስና የሰከሩት አባዱላ ገመዳ፣ የተለያዩ ድርጅቶች ባለቤት ስብሃት ነጋ፣ የቱጃሩን የቢሊዮን ብድር በግል ከመፍቀድ አንስቶ የታዋቂ ባለሃብቶች <ቀኝ እጅ> የሆኑትና ሚስታቸውን ጭምር በሙስና ያሰማሩት በረከት ስምኦን፣ ሶፍያን አህመድ፣ እንዲሁም ቪላዎችን ከ8 እስከ 10 ሚሊዮን ብር ወጪ በማስገንባትና በማከራየት የአገር ሃብት የሚዘርፉ ሁሉም የገዢው ትላልቅ ባለስልጣናት የሙስና ጉዳይ በዋቢነት ይጠቅሳሉ። ባጠቃላይ የስርአቱ ቁንጮዎች የሚያናቁራቸው የገዛ ጥቅምን ከማስጠበቅና አንዱ ጎራ ከሌላው በልጦ በሙስና የሚከብርበትን መንገድ ለማመቻቸት ብሎም ሌላኛውን በመጨፍለቅ ስልጣኑን ከነታማኝ ተከታዮቹ አስጠብቆ የሚቀጥልበትን ብቻ እንደሚያልም የጠቆሙት ምንጮቹ፣ ስርአቱ የአስተዳደር፣የፖለቲካ፣ የፖሊሲ…ወዘተ ልዩነት እንደሌለበት ያሰምሩበታል።

ሌላው ዘብጥያ የወረዱት ባለሃብት አቶ ነጋ ገ/እግዚያብሄር ናቸው፤ የአቶ ነጋ ባለቤት የቀድሞ የሜጋ ኪነጥበብ ሃላፊ እቁባይ በርሄ እህት ናት። ከጥቂት ወራት በፊት ከሙስና ጋር በተያያዘ አስገራሚ ፍርድ የተሰጠውና ጥፋተኛ ተብሎ የተለቀቀው እቁባይ ያንን አይን ያወጣ «ፍርድ» እንዲያገኝ የተደረገው ከአዜብ በተሰጠ ቀጭን ትእዛዝ ነው ያሉት ምንጮቹ ይህ ሊሆን የቻለው አዜብ ከአቶ ነጋ ጋር ባላቸው የቢዝነስ ትስሥር ጭምር መሆኑን አያይዘው ይገልፃሉ። (ሌላም አሳፋሪ ቁርኝት ቢኖራቸውም ለጊዜው ማለፍ ይመረጣል)…

በሌላም በኩል የስዬ አብርሃ ወንድም ምህረተአብ አብርሃ እንዲሁም አይነስውሩ አስመላሽ ወ/ስላሴ ይጠቀሳሉ፤ ምህረተአብ ከስዬ ጋር ተፈርዶበት የተለቀቀው ከአምስት አመት በፊት ሲሆን አሁን ደግሞ ከነገ/ዋህድ ክስ ጋር በተያያዘ አብሮ እንዲቀላቀል ተደርጎዋል።…. አይነስውሩ አስመላሽ (በቅፅል ስማቸው አባይ ነብሶ) በፓርላማ የሕግ ጉዳይ ቢሮን ሲመሩ የቆዩ ናቸው፤ በሕወሐት ክፍፍል ጊዜ እያለቀሱ ፓርቲው እንዳይፈርስ ሲማፀኑ እንደነበር ያስታወሱት ምንጮቹ በተለይ በአንድ ቀን ተፅፎ እንዲወጣ የተደረገውንና አንድ ሰው ለማጥቃት ሲባል ብቻ አዋጅ ሆኖ እንዲፀድቅ የተደረገውን ዋስትና የሚከለክል ሕግ ካረቀቁት አንዱ እንደሆኑ ይገልፃሉ። የአስመላሽ ባለቤት በጠ/ሚ/ሩ ቢሮ ተመድባ በፀሓፊነት የቆየችና በተለይ «ሚስጥራዊ» የሚባሉ ዶክመንቶችንና የአቶ መለስ ፅሁፎችን (በብእር ስም ይወጡ የነበሩትን ጭምር) በመተየብ በታማኝነት ስታገለግል እንደቆየች አመልክተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በመከላከያ ጄኔራሎችና የበታች ከፍተኛ መኮንኖች ግምገማ ላይ መሆናቸው ታውቋል። ከጥቂት ወራት በፊት ለመጠቆም እንደተሞከረው የሚባረሩ ጄኔራሎች እንዳሉ መገለፁ ይታወሳል። በዚህ መሰረት ከአዜብ ጋር የከረረ ፀብ ውስጥ የገቡት ጄ/ል ታደሰ ወረደን ጨምሮ ሶስት የሕወሐትና ሁለት የብአዴን ጄ/ሎች በሳሞራ ውሳኔ መባረራቸውን ምንጮች ገልፀዋል። በቅርቡ የተጀመረውና « የመለስን ራዕይ እናስፈፅማለን» በሚል መሪ አጀንዳ የቀጠለው ግምገማ ተጨማሪ የመከላከያ የጦር አዛዦችንና የበታች መኮንኖችን ለማባረር ቅድመ ዝግጅት አድርጎ ማጠናቀቁ ታውቋል። በሳሞራ የተወሰነው ሌላው ጉዳይ ለመከላከያ ከሩሲያ የመጡ የመሳሪያ ባለሙያዎች በተለያዩ ቦታዎች እንዲመደቡ መደረጉ ሲታወቅ ይህም የሆነው « አገሪቱ ውስጥ ችግር ከተፈጠረ ልንቋቋም አንችልም » በማለት ሳሞራ ድምዳሜ ላይ በመድረሳቸውና ከአየር ሃይል አንስቶ ያለው ወታደራዊ ክፍል እምነት ሊጣልበት ባለመቻሉ እንደሆነ ምንጮቹ አስረድተዋል። የጦር ሃይሎች ጠ/አዛዥነቱ ስልጣን የጠ/ሚ/ሩ እንደሆነ ሕገ መንግስቱ ቢደነግግም ነገር ግን ለአቶ ሃ/ማርያም ይህ ስልጣን እንዳልተሰጣቸው፣ ጄ/ሎች ሲባረሩ ከእርሳቸው እውቅና ውጭ እንደሆነ፣ ውሳኔው በሳሞራ እንደሚከናወን ምንጮቹ አስረድተዋል።

ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በቁጥሮች

$
0
0

ከይርጋ አበበ

26 : 38 በስታዲየሙ የተሰቀለው የውጤት ማሳያ ኤሌክትሮኒክስ ሰሌዳ የፈርጉሰንን ከኦልድ ትራፎርድ መለዬት በማስመልከት ያስነበበው ጽሑፍ ነው ።ለዚህ ጽሑፌ ርዕስ ያደረኩት ይህ ቁጥር አሰልጣኙ በክለቡ የቆዩባቸውን ዓመታት እና ያገኟቸውን ዋንጫዎች ብዛት ለመግለፅ የተጠቀሙበት ገለፃ ነው።
በሃያ ስድስት ዓመታት የተገኙ ሰላሳ ስምንት ዋንጫዎችን ወደ ክለቡ የዋንጫ መደርደሪያ ማምጣት የቻሉት ሰር አሌክስ ፣ከጨዋታው በኋላ በስታዲየሙ ለታደሙት የክለቡ ደጋፊዎች እና ተጫዋቾች ንግግር አድርገዋል ። በንግግራቸውም እስካሁን በክለቡ ለነበራቸው ቆይታ የተደረገላቸውን እንክብካቤ አድንቀዋል ፤ለክለቡ ውጤት ቀጣይነት ሲባል ለሳቸው የተደረገው ለተተኪው አሰልጣኝም እንዲደረግላቸው ደጋፊዎቹን ተማጽነዋል። ተጫዋቾቹም ለለበሱት ማሊያ ፍቅር እንዲኖራቸው እና ለክለባቸው ውጤት ማማር ጠንክረው እንዲሰሩ አሳስበዋል።
  ህዳር ወር መጨረሻ ላይ ማሰልጠን የጀመሩትን ክለብ ለመሰናበት ጫፍ ላይ የደረሱት አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በማንቸስተር የመጨረሻ ዓመት ቆይታቸው የመጨረሻ ዋንጫቸውን በኦልድ ትራፎርድ ያደረጉትን የመጨረሻ ጨዋታ የዌልሱን ክለብ ሁለት ለባዶ በማሸነፍ መጨረሻቸውን አሳምረው ለመውጣት በቅተዋል።  በታላቁ ኦልድ ትራፎርድ ስታዲየም በልዩ ትዕይንት የተጀመረውና ከሰባ ሺ በላይ ቀያይ ባንዲራዎች አሸብርቆ በከፍተኛ ድጋፍ የታጀበው የእሁድ ምሽቱ ጨዋታ ከሰር አሌክስ በተጨማሪ አንጋፋውን ፖል ስኮልስንም ለሁለተኛ ጊዜ ለመሸኘት የተመቸ አጋጣሚ ነበር።  የሰቀለውን ጫማ በሰር አሌክስ ልመና አውርዶ በማጥለቅ ለቀያይ ሰይጣኖቹ ከፍተኛ አገልግሎትን መስጠት የቻለው ፖል ስኮልስ ከአሰልጣኙ ጋር በክብር ለመሸኘት ችሏል።
  ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በቁጥሮች
fergusen2ፈርጊ ከማንቸስተር ዩናይትድ ጋር ማግኘት የቻሉት የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ብዛት
5 በፈርጉሰን የሰለጠኑቡድኖች ብዛት ሲሆን፡ ኢስት ስቲርሊንግ፣ ሴይንት ሜሪ፣ አበርዲን፣ የስኮትላንድ ብሄራዊ ቡድን እና ማንቸስተር ዩናይትድ
6 በተጫዋችነት ዘመናቸው ሰር አሌክ የተጫወቱባቸው ክለቦች፡ ኩይን ፓርክ፣ ሴይንት ጆንስተን፣ ደንፈርምሊን፣ ፋልክሪክ እና አይር የተባሉ የስኮትላንድ ክለቦች
9 የሰባ አንድ ዓመቱ የቀድሞ የማንቸስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ያገኟቸው የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫዎች ቁጥር አምስቱን በማን ዩናይትድ አራቱን በአበርዲን
26 ስኮትላንዳዊው አዛውንት በኦልድ ትራፎርዱ ክለብ የነበራቸው ቆይታ በዓመት፡- ይህንን ያህል ዓመት ማንቸስተር ዩናይትድን ያሰለጠነ አሰልጣኝ የለም።
38 የእንግሊዙ ክለብ ባለፉት ሃያ ስድስት ዓመታት በሰር አሌክስ ፈርጉሰን አሰልጣኝነት ያገኛቸው ዋንጫዎች ብዛት፡- ይህንን ያህል የዋንጫ ብዛት መደርደሪያው ላይ የሰቀለ አሰልጣኝ ሲቪው ላይ የተፃፈለት አሰልጣኝ ከሰር አሌክስ ውጪ ማንም የለም።
104 ሰር አሌክስ በሃያ ስድስት ዓመታት ቀዩን ማሊያ ለማልበስ ወደ ክለባቸው ያስመጧቸው ተጫዋቾች፡- ለመጨረሻ ጊዜ ያስፈረሙት ትውልደ አይቮሪኮስታዊው ክሪስቶፎር ዛሃ ሲሆን ባለፈው ጃንዋሪ ወር በተከፈተው የተጫዋቾች ዝውውር በ15ሚሊዮን ፓውንድ ገዝተው ለአሳዳጊ ክለቡ በውሰት ሰጥተውታል። በፈርጊ ተገዝቶ ለፈርጉሰን ቡድን መጫወት ያልቻለ ተጫዋች።
170 ውጤታማው አሰልጣኝ በተጫዋችነት ዘመኑ ለተሰለፈባቸው ክለቦች ያስቆጠሩት ግብ ድምር፡-  ፈርጊ ላለፉት ሃያ ስድስት ዓመታት ወደ ማንቸስተር ካዘዋወሯቸው 104 ተጫዋቾች ውስጥ የሚበዛውን ቁጥር የሚይዙት አጥቂዎች መሆናቸው አሰልጣኙ ውጤታማ የአጥቂ መስመር ተጫዋች እንደነበሩ ማሳያ ነው ሲሉ የሚያውቋቸው ይናገራሉ።
370 ቁምጣና ማሊያ ለብሰው ወደ ሜዳ የገቡበት የጨዋታ ብዛት፡- ለስድስት ክለቦች በአጠቃላይ መሰለፍ የቻሉት የጨዋታ ብዛት 370 ብቻ ሲሆን በነዚህ ጨዋታዎች 170 ግቦችን ማስቆጠር መቻላቸው እውነተኛ የጎል ማሽን ነበሩ ያስብላል።
1499 ማንቸስተር ዩናይትድን እየመሩ ወደሜዳ የገቡባቸው ጨዋታዎች፡- ከሳምንት በኋላ 1500ኛ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ሲሆን፡- እስካሁን ግን 1499 ጨዋታዎችን አድርገው 895ቱን ማሸነፍ ችለዋል።
የፈርጉሰን ምርጥ አስራ አንድ
የእንግሊዙ ዘ ኢንዲፔንደንት ጋዜጣ የሃያ ስድስት ዓመት የሰር አሌክስ ፈርጉሰንን ምርጥ 11 ፈራሚዎች እንዲመረጡ በበተነው መጠይቅ መሰረት የአብላጫውን ድምፅ ያገኙትን አስራ አንድ ተጫዋቾች እንዲህ እናቀርባቸዋለን።
1. ፒተር ሺማይክል ምርጡ የፈርጊ ግብ ጠባቂ
2. ጋሪ ኔቭል ዝምተኛው ጀግና
3. ፓትሪስ ኢቭራ የፈርጉሰንን ክፍተት የደፈነ ምርጥ የኋላ መስመር ተጫዋች
4. ያፕ ስታም ደፋር እና አይደክሜ ሆላንዳዊ
አማካይ መስመር
5 . ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለማችን ውዱ ተጫዋች የፈርጊ ምርጥ ፖርቹጋላዊ ፈራሚ
6 . ሪያን ጊግስ የአንድ ክለብ ማሊያ ብቻ ገላው የለመደው ዌልሳዊ ምርጥ ባለ ግራ እግር
7 . ሮይ ኪን አየርላንዳዊው ጉልበተኛ በማንቸስተር አሻራው የማይተካ ሚና ነበረው
8. ፖል ስኮልስ ምርጡ እንግሊዛዊ ለፈርጉሰን ቡድን ያልከፈለው አልነበረም
የአጥቂ መስመር
10. ዋይኒ ማርክ ሩኒ በማንቸስተር ያለው ቆይታ ያልተረጋገጠው የኤቨርተን አካዳሚ ፍሬ ከምርጦቹ የፈርጊ ፈራሚዎች አንዱ ለመሆን ጊዜ አለፈጀበትም
11. ኤሪክ ካንቶና የአንድ ሚሊዮን ፓውንድ ወጪ የሆነበት ፈረንሳዊ አመለ ብልሹ ከ1995-98 የማንቸስተር ዩናይትድ ውጤት ግምባር ቀደም ተጠቃሽ ነበር።

የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠርጣሪዎቹ ላይ በጥንቃቄ የታጀበ መግለጫ ሰጠ

$
0
0
·        ተጠርጣሪዎቹን ለመያዝ የታሰበው ከአቶ መለስ ህልፈት በፊት ነው
·        ተጨማሪ እርምጃ እንደሚወሰድ ኮሚሽነሩ ፍንጭ ሰጥተዋል
·        በተጠርጣሪዎቹ ላይ የተወሰደው እርምጃ ታስቦበት እንጂ
በግርግር አይደለም ብለዋል
በዘሪሁን ሙሉጌታ 
Commissionየፌዴራል የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ዓሊ ሱሌይማን ሰሞኑን በድንገት በቁጥጥር ስር በዋሉት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና ባለሀብቶችን በተመለከተ በጥንቃቄ የተሞላ መግለጫ ሰጡ።
በመግለጫው ላይ በርካታ ጋዜጠኞች ተገኝተው ለኮሚሽነሩ በርካታ ጥያቄዎች ለማቅረብ ቢፈልጉም ጋዜጣዊ መግለጫው በአጭሩ እንዲከናወን ተደርጓል። በዚሁ ጥንቃቄ በተደረገበት መግለጫ ላይ ኮሚሽነር ዓሊ ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ ጥናትና ክትትል ሲደረግ የቆየው ከሁለት ዓመት በፊት አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ወቅት መሆኑን አረጋግጠዋል። ኮሚሽኑ በቀጣይም እርምጃ እንደሚወስድ ፍንጭ የሰጡ ሲሆን በተጠርጣሪዎቹ ላይ የተወሰደው እርምጃ ታስቦበት እንጂ “በቱማታ” አይደለም ሲሉ ተናግረዋል።
ችግሩ የቆየ ከሆነ አሁን ለምን እርምጃ ተወሰደ ተብለው የተጠየቁት ኮሚሽነሩ ሲመልሱ፤ “ጠመንጃ የያዘ ሰው “ኮሽ” ባለ ቁጥር አይተኩስም” እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ግምት ውስጥ መግባት ያለባቸው ጉዳዮች ነበሩ። ከነዚህም ውስጥ ደግሞ የዜጎችን ሕገ-መንግስታዊ መብት ሳይነካ በቂ ማስረጃ መሰብሰብ በማስፈለጉ ነው” ብለዋል። ሙስናም ቀጣይ ትግል በመሆኑ እርምጃው ዘግይቷል ሊባል አይቻልም ሲሉ ተናግረዋል። በሌሎችም መስሪያቤቶች ክትትሉ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።
“ትልልቅ የመንግስት ኃላፊዎችን መያዝ ድፍረቱ ከዬት ተገኘ?” ለሚለው የጋዜጠኞች ጥያቄ ኮሚሽነሩ ሲመልሱ ከዚህ በፊትም ትላልቅ የመንግስት ኃላፊዎች ክስ ሲመሰርት መቆየቱን ጠቅሰው የኮሚሽኑ ትኩረት ወንጀሉ ላይ እንጂ ግለሰቦቹ ላይ አለመሆኑን ተናግረዋል።
በቂ ማስረጃ ካላችሁ ለምን ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ መጠየቅ አስፈለጋችሁ ለተባሉት ኮሚሽነሩ ሲመልሱ ይዞ ለመመርመር የሚያበቃ ማስረጃ እና ለፍርድ ቤት አሳማኝ ማስረጃ ማቅረብ የተለያዩ በመሆኑ ነው ብለዋል።
የተጠርጣሪዎቹን ልጆች (ተማሪዎች) ለምን ያዛችሁ ለሚለው ጥያቄም የማውቀው ነገር የለም ብለዋል። ምርመራውም በተጠርጣሪዎቹ ላይ ብቻ እንደሆነ ገልፀዋል።ali
በቁጥጥር ስር ከዋሉ ተጠርጣሪዎች መካከል ያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ ለምን አሰራችሁ? ተብለው ኮሚሽነሩ ቢጠየቁም ያለመከሰስ መብት ሊነሳ ይችላል በሚል ብዙም ግልፅ ያልሆነ መልስ ሰጥተዋል።
ተጠርጣሪዎቹን ለመያዝ የባለሥልጣናት የሐብት ምዝገባው አግዟችኋል ወይ ለተባሉት “አግዞናል” በሚል አጭር መልስ ሰጥተዋል። ወደፊትም በግብር ጉዳይ ላይ ኮሚሽኑ ያተኩራል ብለዋል። እርምጃው የፖለቲካ ጉዳይ ስለመሆኑም ተጠይቀው በሀገራችን ብቻ ባይሆን በሌሎች አገሮችም የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣን ሲያዙ ጉዳዩ “ፖለቲካ ነው” መባሉ አይቀርም። ወደፊት የፖለቲካ ኬዝ እንዳልሆነ በፍርድ ቤቱ ውሳኔ እናሳያለን በማለት በአጭሩ መልሰዋል።
ከሀገር ውጪ ስለኮበለለ ሀብትም ተጠይቀው ለጊዜው አስፈላጊ አይደለም። ነገር ግን በርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ተጋግዘን እንሰራለን ሲሉ መልሰዋል።¾  (ምንጭ  ሰንደቅ ጋዜጣ የዛሬ ዕትም)

በሙስና ተጠርጥረው የታሰሩት ‘‘አያያዛችን ህገ-መንግስታዊ ሥርዓቱን የተከተለ አይደለም’’ አሉ (የፍርድ ቤት ውሎ)

$
0
0
‘‘አያያዛችን ህገ-መንግስታዊ ሥርዓቱን የተከተለ አይደለም’’
ተጠርጣሪዎች
*‘‘እስካሁን ተከሳሽ የሚባል የለም፤ እነዚህ ሰዎች ተጠርጣሪዎች ናቸው’’
ፍርድ ቤቱ
*‘‘በሚዲያ የሚተላለፈው ሪፖርት በቤተሰቦቻችን ላይ ጫና እየፈጠረ ነው’’
ተጠርጣሪዎች
በአሸናፊ ደምሴ
Melaku-Fenta-and-Gebrewahid-Woldegiorgisበሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የፌዴራሉ ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን መርማሪዎች ማጣራት እያካሄዱባቸው የሚገኙት 24 ግለሰቦች የዋስትና መብታቸውን በተመለከተ በትናንትናው ዕለት የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ውሳኔ ተሰጣቸው።
በትናንትናው ዕለት የኮሚሽኑ መርማሪ በሦስት ክሶች ከፋፍሎ ክስ የመሰረተባቸው 24 ተጠርጣሪዎች በፍርድ ቤቱ የተገኙ ሲሆን፤ ከትናንት በስቲያ በነበረው የቃል ክርክር ወቅት ተነስቶ የነበረውን የዋስትና ጥያቄ ምላሽ ተሰጥቶበታል። በዚህም የፌዴራል ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ ሕገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ ከምክር ቤት አባልነታቸው መታገዳቸውን የሚያስረዳ ደብዳቤ ሊቀርብ ይገባል ያለው ፍርድ ቤቱ፤ ይህንንም ለማጣራት ለግንቦት 9 ቀን 2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በመሆኑም በአንደኛ ክስና በሁለተኛ ክስ ስር የተዘረዘሩት ተጠርጣሪዎች በሙሉ ለግንቦት 19 ቀን 2005 ዓ.ም የምርመራው ፈቃድ ፀንቶባቸው የተቀጠሩ ሲሆን፤ አቶ መላኩ ፈንታን ጨምሮ በናዝሬት ጉምሩክ ባልደረቦች ስር የተጠረጠሩት ግለሰቦች ለግንቦት 9 ተቀጥረዋል።
በፌዴራሉ የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን መርማሪዎች በናዝሬት ጉምሩክ ባልደረቦች ላይ የተለያዩ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ወደሀገር ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ ያልተገባ ሀብት አግኝተዋል ሲል ክሱን የዘረዘረ ሲሆን፤ ከስድስቱ ተጠርጣሪ መካከል ሁለቱ ብቻ ጠበቆቻቸውን ማግኘታቸውን በመጥቀስ ቀሪዎቹ ከጠበቆች ጋር እንዳልተገናኙ በመግለፅ ለፍርድ ቤቱ ያስረዱ በመሆናቸው፤ ፍርድ ቤቱም ከጠበቆቻቸው ጋር እንዲገናኙና ሀሳባቸውን አደራጅተው እንዲቀርቡ በማለት ለግንቦት 9 ቀን 2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ፍርድ ቤቱ ከትላንት በስቲያ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ተጠርጣሪዎቹ ለምን ከጠበቆች ጋር አልተገናኙም ለሚለው የፍርድ ቤቱ ጥያቄ በተሰጠው ምላሽ፤ በማረሚያ ቤት የሚገኙ ሰዎች ረቡዕና አርብ ብቻ በጠበቆቻቸው ጋር የሚገናኙበት አሰራር መኖሩ ተብራርቷል። በዚህም ላይ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጠው በመጠየቅ ለግንቦት 9 ቀን 2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ፍርድ ቤት ከቀረቡት ተጠርጣሪዎች መካከል አብዛኞቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጉዳያቸውን ያስረዱ ሲሆን፤ ስለተከሰስንበት ወንጀል በቅጡ የምናውቀው ነገር የለም። አያያዛችን ህገ-መንግስታዊ ሥርዓቱን የተከተለ አይደለም። ሰሞኑን በሚዲያ እየተነገረ ያለው ነገር ትክክል ያልሆነና የቤተሰቦቻችንን አንገት ያስደፋ ነው ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ፍርድ ቤቱ በበኩሉ ‘‘በምንም መልኩ ቢሆን እስካሁን ተከሳሽ የሚባል ነገር የለም፤ እነዚህ ሰዎች ተጠርጣሪዎች ናቸው’’ ሲል ዐቃቤ ሕግ ክስ ባልመሰረተበት ሁኔታ ተጠርጣሪዎቹ በተሳሳተ ስም መጠራት የለባቸውም ብሏል።
በኮሚሽኑ መርማሪዎች ሁለተኛ ክስ ስር የፌዴራሉ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስን ጨምሮ ባለቤታቸው ኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋዬ እና እህታቸው ወ/ሮ ንግስት ተስፋዬን ከነልጅዋ እንዲሁም ሌሎች በድምሩ 12 የሚደርሱ ተጠርጣሪዎች የቀረቡ ሲሆን፤ የተጠረጠሩበት ወንጀልም ወደሀገር ውስጥ እንዳይገባ የተከለከለን ሲሚንቶ እንዲገባ በማድረግ፣ በኮንትሮባንድ የተሰማሩ ሰዎችን በማገዝ፣ ከተጠርጣሪዎችም መካከል የሁለቱን ክስ የሚደግፉ ሠነዶችን ማሸሽ በሚሉ ወንጀሎች እጠይቃቸዋለሁ ይላል።
አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ በጠበቃቸው አማካኝነት እንዳስረዱት ‘‘ቤተሰቤ ተበትኗል፤ ልጄ ለትምህርት የሚገለገልበት ላፕቶፕ ተወስዶበታል። ባለቤቴንም ህጉን ባልተከተለ መንገድ ልብስ አስወልቀው ጭምር ፈትሸዋታል፤ ልታሸሽ ነበር ተብሎ የተያዘውም ካርታ ፎቶ ኮፒው መሆኑንና ዋናው በፌዴራሉ ሥነ-ምግባና ፀረ-ሙስና መርማሪዎች እጅ እንደሚገኝም ጭምር አስረድተዋል።
በሌላም በኩል ተጠርጣሪዎቹም በማረሚያ ቤት የተቀበላቸው አያያዝ መልካም አለመሆኑን በመጥቀስ ለፍርድ ቤቱ ያስረዱ ሲሆን፤ ፍርድ ቤቱም ተጠርጣሪዎቹ በማረሚያ ቤት ቆይታቸው ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸው እንዲጠበቅላቸው ሲል ትዕዛዝ ሰጥቷል።
የፌዴራሉ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መርማሪ ቡድን በሙስና ተጠርጥረው ጉዳያቸውን ለፍርድ ለማቅረብ በተሰናዳባቸው 24 ግለሰቦች ላይ ሦስት ክሶችን የመሰረተ ሲሆን፤ በ1ኛ ክስ ስር በእነ አቶ መላኩ ፈንታ መዝገብ ውስጥ የሚገኙት 7 ተጠርጣሪዎች አቶ እሸቱ ወ/ሰማያት፣ አቶ መርክነህ አለማየሁ፣ አቶ አስመላሽ ወ/ማርያም፣ አቶ ከተማ ከበደ፣ አቶ ስማቸው ከበደ እና ዶክተር ፍቅሩ ማሩ ይገኙበታል። እነዚህ ቀረጥና ታክስን በማጭበርበርና አራጣ በማበደር የተከሰሱ ግለሰቦች እንዲቋረጥ በማድረግ ወንጀል ተከሰዋል።
በሁለተኛው የክስ ዝርዝር ውስጥ አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስን ጨምሮ አቶ በላቸው በየነ፣ አቶ ጥሩነህ በርታ፣ አቶ ተስፋዬ አበበ፣ አቶ ነጋ ገ/እግዚአብሔር፣ አቶ ምህረተአብ ካሳ፣ አቶ ሙሌ ጋሻው፣ አቶ አሞኘ ታገለ፣ ኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋዬ፣ አቶ ሀብቶም ገብረመድህን እና ወ/ሮ ንግስቲ ተስፋዬን ጨምሮ በመጨረሻ የተቀላቀሉትን 12ኛ ተከሳሽ አቶ ተወልደ ብስራትን ያጠቃልላል። በዚህም ክስ ስር ተጠርጣሪዎቹ ፈፀሙት የተባለው ወንጀል ወደሀገር ውስጥ እንዳይገባ የተከለከለን ሲሚንቶ እንዲገባ በማድረግ፣ በኮንትሮባንድ የተሰማሩ ግለሰቦችን በማገዝ፣ ከተጠርጣሪዎች መካከል የሁለቱን ክስ የሚደግፍ ሰነድ ለማሸሽ ጭምር የሚል ይገኝበታል።
በሦስተኛ ክስነት የተጠቀሰው የናዝሬት ጉምሩክ ባለስልጣናትን የሚመለከት ሲሆን፤ በዚህም ስር አቶ መሃመድ ኢሳን ጨምሮ 6 ተጠርጣሪዎች የተዘረዘሩ ሲሆን፤ እነሱም አቶ ሰመረ ንጉሴ፣ አቶ ዘሪሁን ዘውዴ፣ ወ/ሮ ማርሸት ተስፋዬ፣ አቶ ሙሉቀን ተስፋዬ እና አቶ ዳኜ ስንሻው ይገኙበታል። የተጠረጠሩበት የወንጀል ክስም በኮንትሮባንድ የተለያዩ ዕቃዎች ወደሀገር ውስጥ እንዲገቡ በማድረግና ያልተገባ ሀብትን ማካበት የሚሉት ይጠቀሳሉ።
በትናንትናው ዕለት በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ጉዳዩን ለመከታተል ከተገኘው በመቶዎች የሚቆጠር ሕዝብ መካከል ወደ ችሎት መግባት የቻለው ጥቂቱ ሲሆን፤ በአዳራሹ ጠባብነት ምክንያት በተለይም ጋዜጠኞች ቦታ ሊያገኙ አለመቻላቸው ትኩረትን ስቦ ነበር። አንዳንድ የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰቦችም ችሎቱ በሰፊ አዳራሽ ቢካሄድ የተሻለ ይሆን እንደነበር አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።n (ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ የዛሬ ሜይ 15 2013 ዕትም)

ለፌደረሽን ምክር ቤት ህገ መንግስት አጣሪ ጉባዔ –ጉዳዩ፤ ህገመንግሰትዊ የመብት ጥሰት ስለተካሄደብን የቀረበ አቤቱታ

$
0
0
Federation Council and Regional Government

Federation Council and Regional Government

ለፌደረሽን ምክር ቤት ህገ መንግስት አጣሪ ጉባዔ
እንደሚታወቀው እኛ ባለፈዉ አመት ከመጋቢት እስከ ሰኔ 2004 ዓም ድረስ ከመኖሪያ ቀያችን ከደቡብ ኢትዮጵያ ስንባረር የነበርን ዜጎች ነን:: የመባርርና የመገፋታችን ጉዳይ ግን እስከ አሁን 2005 ዓም ድረስ ቀጥሎአል:: በቅርቡም የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ከልዩ ልዩ ቦታዎች በህገወጥ መንገድ እየተፈናቀልን ስላለነዉ አማሮች በፓርላማ ተጠይቀዉ ሲመልሱ ማንኛዉም ዜጋ በየትኛዉም የኢትዮጵያ ክልል የመኖር ህገ መንግስታዊ መብት እናዳለዉ ገልጸዉ በእኛ ላይ እየተወሰድ ያለዉ እርምጃ ግን ጸረ ህገ መንግስት መሆኑን አስረግጠዉ ተናገረዋል::

 የቀረበውን አቤቱታ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

 

 

5 ሰዓታትን በቀድሞ ማዕከላዊ ፖሊስ (ፍሬው አበበ በአዜብ መስፍን ክስ ከተመረመረ በኋላ የፃፈው)

$
0
0

ፍሬው አበበ

የሰንደቅ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ
ጋዜጠኛ ፍሬው አበበ

ጋዜጠኛ ፍሬው አበበ

ሰኞ ዕለት ከሰዓት በኋላ የተንቀሳቃሽ ስልኬ አንጫረረ፡፡ ሳነሳው ለስላሳ የሴት ድምጽ ፍሬው መሆኔን ማረጋገጫ ጠይቃኝ ስታበቃ የቀድሞ ማዕከላዊ ስለምፈለግ ደረስ ብዬ መምጣት እችል እንደሆን በፍጹም ትህትና ጠየቀቺኝ፡፡ በዕለቱ እንደማይመቸኝ፤ ዕረቡ ጠዋት ግን መገኘት እንደምችል ለደዋዬ ነግሬ ሰልኩን ዘጋሁ፡፡ እንግዲህ በፕሬስ ክስ ጉዳይ ለፖሊስ ቃሌን ስሰጥ ይኸኛው ለአራተኛ ጊዜ መሆኑ ነው፡፡ ከቀድሞዎቹ ሶስት ክሶች አንዱ የስም ማጥፋት ሲሆኑ ሌላኛው በተሰረዘ ፈቃድ ሰርታችሃል፣ ሌላው ደግሞ ያለፈቃድ ጋዜጣ ታትማላችሁ የሚል ነበር፡፡ በአጋጣሚ ሁለቱ የቀድሞ ክሶች ከፖሊስ ያላለፉ ሲሆን አንደኛው ማለትም የኒቲ የኒቨርሲቲ ያሳትመው የነበረው “ኤቢቢአይ ዊክሊ” የተባለው ጋዜጣ በተሰረዘ ፈቃድ ሰርታችሃል በሚል ክስ ከተመሰረተባቸው 14 ያህል ሰራተኞች አንዱ ሆኜ አንድ ዓመት ተኩል ጊዜያት ያህል ፍ/ቤት ከተመላለስኩ በኋላ እኔን ጨምሮ 13 ተከሳሾችን ፍ/ቤቱ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ ይሰናበቱ ሲል ውሳኔ በመስጠቱ ነጻ መሆን ችያለሁ፡፡ (እዚህ ምድብ ውስጥ የአዲስ ነገሩ አብርሃም በጊዜው ይገኝበት ነበር)
ዛሬ ረቡዕ በጠዋት ማልጄ በመነሳት ቁርስ ቀማምሼ ወደተጠራሁበት የቀድሞ ማዕከላዊ ፖሊስ 3፡15 ሰዓት ላይ ደረስኩ፡፡ ማልጄ መነሳቴ ወድጄ አልነበረም፤የሄድኩበትን የምርመራ ጣጣ ከምሳ በፊት ባጠናቅቅ በሚል ጉጉት ነበር ፤አልሆነም እንጂ፡፡ መርማሪዬ ትሁት ሴት ፖሊስ መሆኑዋ ጭንቀቴን ለጊዜውም ቢሆን እንድረሳ ረድቶኛል፡፡ ያው የተለመደውን አሰልቺ ቅጽ መሙላት ግን የግድ ነበር፡፡ ሙሉ ስም፣አድራሻ፣የእናት ሙሉ ስም፣የአባት ሙሉ ስም፣የትውልድ ቦታ፣ የትውልድ ቦታ አድራሻ፣ብሔር፣የባለቤቴ ስም፣አድራሻ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ስም፣የት/ቤቱ አድራሻ፣የተማርኩበት ጊዜ፤የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ስም፣አድራሻ፣ የተማርኩበት ጊዜ፣ የከፍተኛ ትምህርት የተማርኩበት ዩኒቨርሲቲ ስም፣አድራሻ፣የተማርኩበት ጊዜ፣የቀድሞ መ/ቤት ስም፣የነበረኝ ኃላፊነት፣የነበረኝ ደመወዝ መጠን፣ የአሁን መ/ቤት ስም፣ያለኝ ኃላፊነት፣ያለኝ የደመወዝ መጠን፣ የጋብቻ ሁኔታ፣የልጆች ብዛት፣ዕድሜያቸው፣አጠቃላይ ክሱ እና በክሱ ላይ ያለኝ ምላሽ፣ የተጠረጠርኩበትን መፈጸም አለመፈጸሜን (የእምነት ክህደት ቃል) ወዘተ….እጅግ አድካሚ ዶሴ ተሞላና ጨረስኩ ስል አሻራና ፎቶግራፍ መነሳት የግድ ነው ተባልኩ፡፡ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ሰጥቻለሁ ብልም ሰሚ አልነበረም፡፡ እዚያም የእያንዳንዱ ጣት አሻራ(የግራ የቀኝ) ፣ ፎቶ ፊትፊት በግራና ቀኝ መነሳት ግድ ነበር፡፡ ይህ ሁሉ ግን በፕሬስ ተፈጸመ ተብሎ በአንድ ሰው በቀረበ አቤቱታ መነሻነት ገና ለገና ተጠርጣሪ ነው የተባለው ፕሬስ ዋናአዘጋጅ የመጀመሪያዋ ቀላል ፈተና መሆኑ ነው፡፡
ፖሊስ ቃል ከመስጠቴ በፊት ሁለት ጥያቄዎች እንዲመለሱልኝ ለመርማሪዬ ጥያቄ አቀረብኩኝ፡፡ አንዱ የተከሰስኩበት ጉዳይ እና ከሳሼ ማን እንደሆነ ነበር፡፡ የተከሰስኩበት ጉዳይ በቀድሞው ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከቤተመንግስት አለመውጣታቸውን ጠቅሰህ ጽፈሃል፣በዚህ ስም አጥፍተሃል የሚል ይዘት ያለው መሆኑ ተነገረኝ፡፡ ዜናው የተሰራው በአበሻ አቆጣጠር መስከረም 30 ቀን 2005 ዓ.ም ሲሆን በጠቅላው ወደስምንት ወር ገደማ ሆኖታል፡፡

የዜናው ይዘትም በአጭሩ ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከቤተመንግስት አለመውጣታቸውን በአንድ በኩል በሌላ በኩል በወቅቱ ከተሾሙ 19 ቀናት የሞላቸው ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ መኖሪያ ቤታቸው ከሚገኝበት ሳር ቤት አካባቢ በየዕለቱ ትራፊክ እያዘጉ በመውጣትና በመግባት ላይ መሆናቸው፣ የአካባቢውን ህብረተሰብ የመንቀሳቀስ ነጻነት ላይ ችግር መፍጠሩን፣ለደህንነታቸውም ቢሆን አስጊ መሆኑን፣ ወ/ሮ አዜብ መስፍን ቤተመንግስቱን እንዲለቁ በተደጋጋሚ ተጠይቀው ባልታወቀ ምክንያት ፍቃደኛ አለመሆናቸውን የሚያትት ነበር፡፡ ዜናውን ስንሰራው በትልቁ ታሳቢ ያደረግነውና እንደጋዜጠኛ ሙያዊ ነጻነታችን ተወጥተኛል ብለን የምናስበው የጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ስራቸውን ማከናወን በምንም መልኩ ተቀባይነት ያልነበረውና ደህንነታቸውንም በእጅጉ ለአደጋ ያጋለጠ የመሆኑ ጉዳይ ነበር፡፡ የዚህ ዜና መውጣት በአገር ውስጥና በውጪ መነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ ሆኖ በመቆየቱ ወ/ሮ አዜብ በክብር ወደተዘጋጀላቸው ቦታ እንዲዛወሩ፣አቶ ኃ/ማርያምም ወደቤተመንግስት እንዲገቡ በማድረግ ረገድ ሁለቱንም ወገኖችን የጠቀመ ውጤት አስገኝቷል ብለን እናምናለን፡፡ በዚህ ዜና መሸለም እንጂ መጉላላትና ክስ ይቀርብብናል ብለን አስበንም አናውቅም፡፡

ሌላው መርማሪዬን የጠየኳት ጉዳይ ከሳሼ ማን ነው የሚል ነበር፡፡ ይህን ጥያቄ በቀጥታ ለመመለስ አልፈለገችም፡፡ምናልባትም አለቆችዋ እንዳትነግር አስጠንቅቀዋት ሊሆን ይችላል፡፡ እኔ ግን እንደተከሳሽ ቃሌን ለመስጠት ቢያንስ ከሳሼ ማን እንደሆነ የማወቅ መብቴ ሳይከበርልኝ ቀርቷል፡፡ በድፍኑ “ከሳሽ ፖሊስም ሊሆን ይችላል” ተብዬአለሁ፡፡ በስም ማጥፋት ክስ ጉዳይ ግለሰብ ከሆነ ራሱ በሚያቀርበው አቤቱታ፣የመንግስት ሹመኛ ከሆነ በዓቃቤ ሕግ በኩል ክስ ሊቀርብ እንደሚችል ያለውን ድንጋጌ አንስቶ መከራከር እዚህ ቦታ ላይ ዋጋ አልነበረውም፡፡ ያም ሆነ ይህ ከሳሼን የማወቅ መብቴ ተከልክዬ እነሆ ቃሌን ለመስጠት በቃሁ፡፡
 በዚህ ሁኔታ ጠዋት 3፡15 ገደማ የቀድሞ ማዕካዊ የገባሁ የአምስት ሺ ብር ዋስ እስካቀርብ ድረስ የቁም አስረኛ ሆኜ ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ገደማ ግቢውን ለቅቄ ወጥቻለሁ፡፡
ፍሬው አበበ
የሰንደቅ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ

የዓለም ህዝብ ሥጋትና በዚሁ ሥጋት ውስጥ ተተብትባ የተያዘችው ኢትዮጵያ

$
0
0

 Map ethiopiaመንደርደሪያ

 አገራችን  ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ታሪክ በተለይም ከአንደኛው እስከ ስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ህዝቧ

አምልኮ ፈጣሪውን የሚከተልና  የሃገሩን ፤ የወገኑን ክብር ሳያስደፍር የኖረ ታላቅ ህዝብ መሆኑን ያስመሰከረ  እንደሆነ ታሪክ ይመሰክራል ። ክ7ተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ  በዓለም ላይ ክፍተኛ የእድገት ደረጃውን ጠብቆ ሃገሩ በዓለም ዙሪያ እንድትታወቅ  ያደረገ ህዝብ  ለመሆኑ ቛሚ ምስክር የሆኑት ታሪካው ህንጻዎቹ ምስክሮች ናቸው።

ለሃገራችው  የትውልድ ዓርዓያ ሆነው ያለፉት አባቶቻችንም በክብር  ዘውትር በጠላቶች ሲከበሩና ሲፈሩ የኖሩ ለመሆኑ በተደጋጋሚ ዓለም ያወቀው ፀሐይ የሞቀው የታሪክ ህያው ምስክር ነው ። ይህች ሃገር ለመላው  የጥቁር ዘር ኩራት  ሆና በጠላትነት የፈረጁዋት ጠላቶቿን ደግሞ እንደ እሳት  የፈጀች ታላቅና ውድ ሃገር ነች።ይህች ሃገር ለምን እንደሊሎቹ የአውሮፓውያን ሃገራት ለምን  በሥልጣኔ  ወደፊት እንዳልገፋች ኢትዮጵያውያን ስንጠይቅ መልሱ ምን ይሆን?

Download (PDF, 691KB)

 

በምርጫ 97 የትዝታ ማህደር ውስጥ የልደቱ ቦታ

$
0
0

ከመሐመድ አሊ መሐመድ (ጋዜጠኛ)
lidetuእስኪ በትዝታ ፈረስ ሽምጥ እንጋልብና የምርጫ 97ን ሂደት እንደዋዛ እንዳስሰው፡፡ ምርጫ 97 ሲነሳ ከትውስታ ማህደራችን ጎላ ብሎ የሚወጣው የሚያዚያ 30 ትዕይንተ ህዝብ ነው፡፡ ለነገሩማ ያ ታሪካዊ ዕለት እንዴት ይረሳል? ወደ መስቀል አደባባይ የሚያመሩ መንገዶች ሁሉ በለውጥ መንፈስ በተሞላ የህዝብ ጎርፍ የተጥለቀለቁበት፣ ያለማንም ቀስቃሽ ህዝብ ለመብቱና ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ሆ! ብሎ የወጣበት፣ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ብቃት ያረጋገጠበት፣ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ዓለምን ያስደመመበት ያ ታሪካዊ ዕለት እንዴት ይረሳል?
ሚያዚያ 30ን ስናስታውስ አንድ ክስተትም አብሮ ይታወሳል፡፡ “ዴሞክራሲን እናወድስ” በሚል መሪ ቃል መስቀል አደባባይና ዙሪያ ገባውን ባጨናነቀው ህዝብ መሐል አንድት ፒክ-ኣፕ መኪና ወደ አደባባዩ እምብርት ዘለቀች፡፡ በመኪናዋ ላይ በኢትዮጵያ ባንዲራ ደምቆ የለውጥ ሀዋርያነቱን የሚያውጅ ሰው ነበር፡፡ ህዝቡም ያን የለውጥ ሀዋርያ በፍቅርና በስስት ስሜት እጁን ለመንካት ይረባረብ ነበር፡፡ እሱም እጆቹን በማውለብለብ አፀፋና ምስጋናውን ይገልፅ ነበር፡፡ በወቅቱ ስለዚያ የለውጥ ሃዋርያ አንዳች አሉታዊ አስተያየት መስጠት ትልቅ ዋጋ ያስከፍል ነበር፡፡
ከምርጫው በኋላም ያ የለውጥ ሀዋርያ በድርጅቱ ጽ/ቤት ታገተ ተብሎ ህዝቡ በፆም በፀሎት ተጠመደ፡፡ በርካቶች ባገኙት ሚዲያና መንገድ ሁሉ እገታው የፈጠረባቸውን ስሜት በእንባና ሲቃ ሲገልፁ ተደመጡ፡፡ ግና በዚች ምድር ቋሚ ነገር የለምና ያ የለውጥ ሀዋርያ ተብሎ የተወደሰ ሰው ብዙም ሳይቆይ በካሀዲነት ተፈረጀ፡፡ ያ ሰው ማን እንደሆነ ግር የሚለው ሰው ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ያለገደብ የተሞገሰና የተወገዘ! ግን ለምን?
ስለልደቱ አያሌው ብዙ ተብሏል፡፡ እኔ የተባለውን ሁሉ አልጋራም፡፡ ነገር ግን ከፍተኛ የሆነ የስልጣን ጉጉት እንዳላቸው አውቃለሁ፡፡ ቢሆንም የፖለቲካ ትግል የመጨረሻ ግቡ ሥልጣን ይዞ ዓላማን ማስፈፀም በመሆኑ የሥልጣን ጥማት እንደነውር ሊታይ የሚገባው አይመስለኝም፡፡ ነውር የሚሆነው ዴሞክራሲያዊ ባልሆነ መንገድ ሥልጣን ለመያዝ ሲባል የቆሙለትን ዓላማ ጥያቄ ውስጥ እንዲገባ ማድረግ ነው፡፡ በተለይ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማስፈን በሚደረግ ትግል ውስጥ ዴሞክራሲያዊ ባልሆነ መንገድ ሥልጣን ለመያዝ መሞከር የትግሉን ዓላማ ምን ያህል ሊጎዳው እንደሚችል መገመት አያስቸግርም፡፡
ከዚህ አንፃር አቶ ልደቱ በተለያየ ጊዜ ከሥልጣን ሽኩቻ ጋር በተያያዘ ትግሉን የሚጎዱ አፍራሽ እርምጃዎች ወስደዋል፡፡ አቶ ልደቱ በቀድሞው መዐህድ (የመላው አማራ ህዝብ ድርጅት) አመራርና በወጣቶች መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ሳቢያ ድርጅቱን ለቀው ሲወጡ የወሰዱት እርምጃ የድርጅቱን ገፅታ ከማጠልሸቱም በላይ በትግሉም ላይ ቀላል የማይባል ጉዳት አድርሷል፡፡ በኋላም ኢዴፓ ከተቋቋመ በኋላ በፓርቲው መሥራች አባላት መካከል በተፈጠረው አለመግባባት አቶ ልደቱ ተቀናቃኞቻቸውን ለማስወገድ የተከተሉት መንገድ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መቆማቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነበር፡፡ በወቅቱ የሥልጣን ተቀናቃኞቻቸውን የፖለቲካ ሰብዕና ለመግደል/ሽባ ለማድረግ (character assassination/paralization) በእሳቸው ላይ ሲደርስ ያወገዙትን አሉባልታ የመንዛትና ስም የማጥፋት ስልት መከተላቸው አይዘነጋም፡፡
አቶ ልደቱ የራሳቸው ምክንያት ቢኖራቸውም ፓርቲያቸው ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በነበረው የትግልና የትብብር ግንኙነቶች ላይም የሚወስዷቸው አቋሞች እንደዚሁ ትግሉን የሚጎዱ ነበሩ ማለት ይቻላል፡፡ በተለይም በ1997 ዓ.ም በተፈጠረው #ቅንጅት$ ውስጥ አቶ ልደቱ ሲያሳዩት የነበረው ልታይ ልታይ ባይነትና አጉል #ብልጣብልጥነት$ በተቃውሞው ጎራ ውስጥ በዓይነ-ቁራኛ እንዲታዩ ሳያደርጋቸው አልቀረም፡፡ ቅንጅት በ1997 ምርጫ ሂደት በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትና ድምፅ ካገኘ በኋላ ወደ ውህደት ሲያመራ የልደቱን የሥልጣን ፍላጎት ባለማርካቱ በእልህ ተነሳስተው የወሰዱት እርምጃ ታላቅ ታሪካዊ ስህተት ነበር ማለት ይቻላል፡፡ አቶ ልደቱ ለወሰዱት እርምጃ ምክንያት ቢኖራቸውም እርምጃውን የወሰዱበት ጊዜና መንገድ ከህዝብ እንዲነጠሉ በማድረግ ብዙ ፖለቲካዊ ዋጋ አስከፍሏቸዋል፡፡
አቶ ልደቱ ለቅንጅት መፍረስ ምክንያት አለመሆናቸውን ለማሳመን ጥረት ቢያደርጉም በቀላሉ ሊሳካላቸው አልቻለም፡፡ የእሳቸው መከራከሪያ ቅንጅትን አንድ ልደቱ የሚያፈርሰው ከሆነ ከጅምሩም ቅንጅት የሚባል ጠንካራ ኃይል አልነበረም የሚል ነው፡፡ በእርግጥም ይህ ክርክር በደምሳሳው ሲታይ እውነትነት ያለው ይመስላል፡፡ ነገር ግን አቶ ልደቱ በውህደት ስምምነቱ ላይ መሐተም ለማሳረፍ አሻፈረኝ በማለታቸው የኢህአዴግ መንግሥት ያቋቋመው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቅንጅትን የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ለመከልከል ምክንያት አግኝቷል፡፡ አቶ ልደቱና ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወሰዱት እርምጃ ቀደም ብሎ የተቀነባበረ ይሁን በድንገት የተፈጠረ ግጥምጥሞሽ ሊያስረዱን የሚችሉት አቶ ልደቱ ብቻ ናቸው፡፡
አቶ ልደቱ ቅንጅት ከፈረሰ በኋላ #ሦስተኛ አማራጭ$ በሚል ያመጡት የፖለቲካ ፈሊጥ ብዙዎችን ግራ ያጋባና እሳቸውንም ለባሰ የፖለቲካ ክስረት የዳረገ ነው፡፡ በእርግጥ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ አማካይ ቦታ/#ሦስተኛ አማራጭ$ እንደሚያስፈልግ ቢታመንም ይህን አቋም ለማራመድ በወቅቱ አቶ ልደቱ ትክክለኛው ሰው ነበሩ ለማለት አይቻልም፡፡ ምክንያቱም የ1997 ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረው ውጥረት የቅንጅት መሪዎች ለእስር እስከተዳረጉበት ጊዜ ድረስ በገዥው ፓርቲና በተቃዋሚዎች መካከል ለነበረው የተካረረ ግንኙነት አቶ ልደቱ ዋነኛው ተጠያቂ ናቸው፡፡
ስለሆነም #የጭፍን ተቃውሞ$ ፖለቲካን ለማውገዝ/ከማውገዛቸው በፊት አቋማቸውን የቀየሩበትን አሳማኝ ምክንያት ማቅረብና ቀደም ሲል ሲያራምዱት በነበረው የተካረረ አቋም ሳቢያ ለደረሰው ጥፋት ሁሉ ኃላፊነት መውሰድና ይቅርታ መጠየቅ ነበረባቸው፡፡ ይህን ሳያደርጉ ድንገት ተነስተው #ሦስተኛ አማራጭ$ በማለታቸውና የተቃውሞውን ጎራ ተጠያቂ በማድረጋቸው ህዝብ ሊያምናቸው አልቻለም፡፡ ይልቁንም ከገዥው ፓርቲ ጋር ለመሞዳሞድ እንደፈጠሩት ሥልት ተቆጥሮ በካሃዲነት አስፈርጇቸዋል፡፡ አቶ ልደቱ በተሳሳተ ስሌት በእጃቸው ውስጥ የነበረውን መልካም ዕድል ካጡ በኋላ ተስፋ ሳይቆርጡ ቢፍጨረጨሩም እንደዋዛ ያመለጣቸውን ዕድል በቀላሉ መልሰው እጃቸው ውስጥ ሊያስገቡት አልቻሉም፡፡
ይህም ሆኖ ግን አቶ ልደቱ አያሌው በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ሁነኛ ሥፍራ ያላቸውና የሚገባቸውም ሰው ናቸው፡፡ ወደተደራጀ የፖለቲካ ትግል ከገቡ ጀምሮ ያላቸውን ጊዜና አቅም አሟጥጠው ተጠቅመዋል፡፡ በተለይ የ97 ምርጫ ቅስቀሳ በእሳቸው ጫንቃ ላይ ያረፈ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ በምርጫ ቅስቀሳው በአንድ በኩል የገዥውን ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች አንገት ሲያስደፉ በሌላ በኩል የተቃውሞውን ጎራ ደጋፊዎች አንጀት ያርሱ ነበር፡፡
አቶ ልደቱ በትግሉ ውስጥ ያላቸው ቆይታ በአንፃራዊነት አጭር ሊባል የሚችል ቢሆንም ያካበቱት ልምድና እውቀት ቀላል የማይባል ነው፡፡ በእኔ እይታ አቶ ልደቱ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ደርዝ ባለው መንገድ ለመገምገምና ለመተንተን ብቃት ካላቸው ጥቂት ኢትዮጵያውያን ተርታ የሚሰለፉ ናቸው፡፡ በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው አቶ ልደቱ የተቃዋሚ መሪዎችን ቁጥር በአንድ የሚያሳድጉ ሳይሆኑ በኢትየጵያ ፖለቲካ ውስጥ ትርጉም ያለው ሚና መጫወት የሚችሉ ሰው ናቸው፡፡ በእርግጥ አቶ ልደቱ የሚጫወቱት ሚና እንደየሰው አተያይ አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ የ1997 ምርጫን ተከትሎ አቶ ልደቱን የገጠማቸው ከህዝብ የመነጠል ፈተናና ፈተናውን በአሸናፊነት ለመወጣት ተስፋ ሳይቆርጡ ያደረጉት ጥረትም ስለሰብዕናቸው የሚነግረን ቁም ነገር አለ፡፡
አንዳንድ ሰዎች #ልደቱ ወደ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ዳግም ላይመለስ የውድቀት ጽዋውን ተጎንጭቷል$ ሲሉ በኩራት ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን የልደቱ ከህዝብ መነጠል ለተቃውሞው ጎራ ውድቀት እንጅ በኩራት የሚገለፅ ስኬት አይደለም፡፡ የአንዳንዶቻችን በልደቱ ውድቀት መደሰት ከተራ ምቀኝነት ያለፈ ትርጉም ላይኖረው ይችላል፡፡ ልደቱ ሰው ነውና ተሳሳተ፡፡ የሚሳሳተው ደግሞ የሚሰራ እንጅ ከዳር ቆሞ የሚታዘብ አይደለም፡፡
በነገራችን ላይ የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር የቅንጅት መሪዎች ከእስር ከተፈቱ በኋላ የፈፀሙት ስህተት በምንም መመዘኛ ልደቱ ከፈፀመው ስህተት የሚያንስ አይደለም፡፡ ዱሮም ቢሆን ልደቱ የወሰደው እርምጃ የቅንጅትን ውድቀት አፋጠነው እንጅ ውሎ አድሮ ቅንጅትን ከመፈረካከስ የሚታደገው ኃይል አልነበረም፡፡ ምክንያቱም የቅንጅት አፈጣጠርም ሆነ የሰው ኃይል ጥንቅር ረጅም ርቀት መጓዝ የሚያስችለው አልነበረም፡፡
እንደአለመታደል ሆኖ በቅንጅት ጥላ ሥር የተሰባሰቡት ሰዎች በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ መተያየት የማይፈልጉና አንዱ ሌላውን ጠልፎ ለመጣል የሚያደቡ ወይም በየጓዳ ጎድጓዳው የሚያሴሩ ስለመሆናቸው መሪዎቹ ከእስር በተፈቱ ማግሥት እውነቱ ገሀድ ሆኗል፡፡ ስለሆነም ለቅንጅት መፍረስ ልደቱን ብቻ ተጠያቂ ከማድረግ ይልቅ ሁላችንም ድርሻ ድርሻችንን መውሰድ ይኖርብናል፡፡ እኔ የድርሻዬን ለማንሳት ዝግጁ ነኝ፡፡ ያ ታሪካዊ ሂደት “ውሾን ያነሳ ውሾ ይሁን” በሚል ብሂል ተሸፋፍኖ መቅረት ያለበት አይመስለኝም፡፡ በግልፅ ልንነጋገርበትና ልንማርበት ይገባል ብዬ አምናለሁ፡፡ ስለተቃውሞው ፖለቲካ መፃኢ ዕድል መነጋገር ካለብን ደግሞ #አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ$ እንዲሉ መሆን የለበትም፡፡

የአንድነት/መድረክ የፖለቲካ ግንኙነት እና የጋራ እንቅስቃሴ ከመቀናጀት እስከ ግንባር ያለው አጠቃላይ ሁኔታ ግምገማ

$
0
0

UDJሚያዝያ 19 ቀን 2005 ዓ.ም የአንድነት ፓርቲ ብ/ም/ቤት ባደረገው ስብሰባ ላይ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት የአንድነት/መድረክ የፖለቲካ ግንኙነት እና የጋራ እንቅስቃሴ ከመቀናጀት እስከ ግንባር ያለው አጠቃላይ ሁኔታ ላይ የተዘጋጀውን ሰነድ ገምግሞ አፅድቋል፡፡ ሰነዱም ለመድረክና ለመድረክ አባል ፓርቲዎች እንዲሰጥ፣ አባላትና ደጋፊዎች እንዲያውቁት እንዲሁም ለህዝቡና ለመገናኛ ብዙሃን እንዲሰራጭ በተባለው ውሳኔ መሰረት እነሆ ሰነዱን አያይዘናል፡፡

ትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!
የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት

ድምጻዊት አበበች ደራራ አረፈች

$
0
0


አርቲስት ደበበ እሸቱ በፌስ ቡክ ገጹ እንደዘገበው፦
ለረጂም ዓመታት በራስ ቴአትር በድምጻዊነት ስትሰራና ለአድማጮችዋ ዜማዎችን ስታቀርብ ኖራ በስተመጨረሻው ወደ እስራኤል ሀገር ከትማ ስትኖረ የነበረችው ታዋቂዋ ድምጸ መልካሟ አበበች ደራራ ዛሬ ሜይ 16 ቀን ባደረባት ህመም ሳቢያ ሕይወቷ አልፏል፡፡
አበበች ደራራ በሕመም ተይዛ ለበርካታ ወቅት በአልጋ ላይ ከመቆየቷም ባሻገር ጨርሶ ከሰዎች ጋር ግንኙነት አቋርጣ በሽታዋን ለብቻዋ ስታስታምም እንደነበረች በቅርብ የሚያውቋት ይናገራሉ፡፡
የአበበች ደራራ አስከሬን በኖረችበት የቴል አቪቭ ከተማ በዛሬው እለት ከቀኑ 3.00PM ላይ ወደ ቀብር በወዳጅ ዘመዶች ታጅቦ በመሄድ ሥርአተ ቀብርዋም ይፈጸማል፡፡


ባለ ራእዩ ወያኔ/ኢህአዴግ በሙስና ቅሌት እራሱን አጋለጠ

$
0
0

እስክንድር አሰፋ

ከኖርዌይ

601712_579119188786834_121958311_nባለ ራእዩ የወያኔ  መንግስት ባልታወቀ ወይም ሆን ተብሎ በተሰራ የቴክኔክ ብልሽት በዚህ ሰሞን በአባላትና ጀሌዎቹ ላይ ለ22 አመታት ታይቶ በማይታወቅ የሙስና ቅሌት ሰበብ ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እያጎሯቸው ይገኛል። የሚገርመው ደጋፊዎቻቸው ከሐገር ቤት እስከ ዲያስፖራው  ብዙ ሲለፈልፉላቸው ይሰማ ነበር ልማታዊ መንግስታችን፤ ልማታዊ ሚኒስትሮቻችን ፤ ልማታዊው መሪያችን  በማለት ከሰብአዊ መብት ጥበቃ በፊት መንገድ ስራና የአፓርታማ ግንባታ ይቅደም በማለት  መቆሚያና መቀመጫ አሳጥተውን ነበር አሁን ምን ይውጣቸው ይሆን? እንደ ለመዱት ልማታዊ ሙስና ነው ብለው እንዳያስደነግጡን እንፈራለን።
haገራችንን ኢትዮጵያን ወያኔ /ኢህአዴግ ከተቆጣጠራት ጊዜ ጀምሮ ማለትም እ.ኤ.አ ከ1991 ዓ.ም ሐገሪቷንና ህዝቧን በመሳሪያ አግቶ በዘር በሃይማኖት ከፋፍለው  እንዲሁም ከቁጥጥር ውጪ  በሆነ የሰብአዊ መብት እረገጣ እና የኢኮኖሚ ቀውስ አድርሰውባታል አሁንም እያደረሱባትም ይገኛሉ።
ዝባችንም ከተወለደበት እና ካደገበት ቀዬው ሰላምን ፍለጋና ኑሮውን ለመምራት ሲል እግሬ አውጪኝ በማለት ወደ ማያውቅበት ሐገር ለመኖር ሲሰደድ፤ በየበረሐው ሲደበደብ፤ እንዲሁም ሲገደል እና በህይወት እያለ ሰውነቱ እየተቀደደ የውስጥ አካሉ  ሲሸጥ  እያየንና እየሰማንም ነው።
ይህ ሁሉ በደል እና ስቃይ በህዝባችን እየደረሰ ባለበት ጊዜ ስልጣኑን ተቆጣጥረው ያሉት የወያኔ/ኢህአዴግ ባለስልጣናት እኛ እናውቅላችኋለን፤ እናስተዳድራችኋለን በማለት የባለ እራዩን የዘረኛውንና የገንጣዩን መለስ ዜናዊ አመራር  አላማ ለማስፈጸም እጅ ለእጅ ተያይዘን እንሰራለን በማለት በህግ ላይ ህግ በማውጣት ህዝቡ ቀና ብሎ  እንዳያያቸው በተበላሸና በከረፋ የህግ የበላይነት
ስም ህዝቡን በማፈን፤ ለፍትህና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት መስፈን የሚታገሉ ነገር ግን በአሸባሪነት ስም የታሰሩ ጋዜጠኞች፣ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና የእምነት ስርዓታችንንና የሃይማኖት መሪዎቻችንን ምርጫ እምነታችን በሚፈቅደው መንገድ ብቻ እናከናውን ያሉ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ዜጎችን በአሸባሪነት በመወንጀልና በመክሰስ እንዲሁም በዋልድባ ገዳም አባቶቻችንን በማሳደድና በመዝረፍ ሲያሰቃዩ  እነሱ ግን  በቅሌትና በሙስና የሀገሪቷን ሃብት እና ንብረት  ለግል ጥቅማቸው በማዋል እንዲሁም የሀገሪቷን ጥሬ ሃብትና ንብረት ወደ ውጪ በማሽሽ  በውጪ በሚገኙ ዘመዶቻቸው ስምና የነሱ ተባባሪ ወዳጅ መንግስታት ሐገሮች ባንክ ውስጥ በማስቀመጥ ሐገራችንን ኢትዮጵያን  በአለም ታይቶ በማይታወቅ የኑሮ እድገት የኋልዮሽ እሽቅድምድም ውስጥ በማስገባት ለከፋ ችግር አጋልጠዋታል።
እውነት አሁን ወያኔ/ኢህአዴግ ሀገራችንን ኢትዮጵያ ይህን ሁሉ አመታት ከግብረ አበሮቹና ከጀሌዎቹ ጋር በመተባበር ሲያደማትና ሲበዘብዛት  ቆይቶ አሁን  በሙስና ቅሌት ያዝኳቸው በማለት ግብረ አበሮቹን በገሃድ ያጋለጠበትና አሳዶ  ወደ ወይኒ የወረወረበትን  ምክንያት እውነት ለሐገራች ተቆርቋሪነቱን ለማሳየት ይሆን ? ወይስ የማናውቀው መፍረክረክ ተፈጠረባቸው ? ይህንን ጥያቄ  እሱ እራሱ ባለጉዳዩ ይመልሰው ወይም እነሱ እንደ ጀመሩት እራስ በራሳቸው ተበላልተው ያልቁልናል ብለን ዝም ብለን እንመልከት?
እኔ እንደማስበው ወያኔ/ኢህአዴግ በአሁን ሰአት እያረጀ የመጣ ትልቅ የግራር ዛፍ ነው ብዬ አምናለሁ ምክንያቱም ስርአቱ ውስጥ የመፍረክረክ ሁኔታና የመበስበስ ባህሪይ ማሳየቱ ከውስጡ ያሉት ሞተር የነበሩት እራሳቸውን ወደ ማግለል ደረጃ ላይ ደርሰው እያየናቸው ነው ስለዚህ የበሰበሰውን ስርአት በደንብ እንዲበሰብስ አድርጎ የመጣል ሐላፊነት ያለብን ይመስለኛል ለዛም ዋና መፍትሄ የሚሆነው ስርአቱን ፊት ለፊት እና በተለያየ መንገድ የሚታገሉትን ድርጅቶችን ሆነ ግለሰቦችን አንድ በማድረግ ልዩ ነታችንን ትተን በአንድነት መፋለም ያስፈልጋል ብዬ አምናለው ያለ በለዚያ ስርአቱ በሰበሰ አረጀ እራሱ ይወድቃል ብለን ቁጭ ብለን የምንጠብቅ ከሆነ እራሳችን በስብሰን ከዚህ በበለጠ በከፋ  አገዛዝ እንደምንገዛ ጥርጥር የለኝም።
መልክት ለወያኔ ደጋፊዎች 
በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የወያኔን ስርአት የምትደግፉ ወገኑቻችን  በአሁን ሰአት አለማችን በቴክኖሎጂ አድጋ  አንድ ሆናለች  የትም ሆናችሁ የትም ስለ ሃገራችሁም ሆነ ስለምትፈልጉት ነገር ቤት ቁጭ ብላችሁ ማየትም መስማትም ትችላላችሁ  ስለዚህ ማሳሰብ የምፈልገው ነገር ሐገራችን ኢትዮጵያ ከየት ወዴት እንደምትሄድ እና በስርአቱ ውስጥ ምን ያህል እንዝላልነትና ሐላፊነት የጎደለው አገዛዝ እንዳለ ለናተም የተደበቀ ነገር ያለ አይመስለኝም እድሜ ለቴክኖሎጂ የለፈውን እንተወውና አሁን በቅርቡም በመገናኛ ቦዙሃን እንደሚደመጠው በሐገራች ላይ ምን ያህል ምዝበራና ዘረፋ እየተካሄደባትና ኢ ሰብአዊ ድርጊት በህዝባችን ላይ እየደረሰ እንደሆን ለናተ መንገር  ለቀባሪው አረዱት ማለት ነው  ስለዚህ ጠንቅቃችሁ ታቁታላችሁ ። እግዚአብሄር በሰጣችሁ ጭንቅላት በመጠቀም ወደ ሰውኛ አስተሳሰብ ተመልሳችሁ ጊዜው  ሳይረፍድ ከጭቁኑ ኢትዮጵያዊ ጋር ጎን ለጎን በመቆም በአፓርታይድ አገዛዝ ስር የወደቀችውን ሐገራችንን ነጻ ለማውጣት እንታገል   በማለት ወንድማዊ መልእክቴን አስተላልፋለሁ።
መረጃ ለማግኘትም ሆነ ለግንዛቤ ሰሞኑን ከወጡት ዜናዎች መካከል በጥቂቱ
ቸር ያሰማን
ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሄር ትዘረጋለች
 ድል ለኢትዮጵያ ሞት ለወያኔ

ሰውየው (ክፍልሁለት) ከይገርማል ታሪኩ

$
0
0


ከይገርማል ታሪኩ

Pen-4ሻለቃ ሀይለየሱስ እጅጉ መዐሕድን  ሲቀላቀሉ ድርጅቱ በአማራው ክልል እግሩን አልሰደደም ነበር:: ችግሩ ፋታ የሚሰጥ አይደለም:: አማሮች ካለአለሁ ባይ: ካለአይዟችሁ ባይ እየተጨፈጨፉ ነው:: በቀልን ሰንቆ ከበረሀ የተነሳውና ስልጣኑን ሙሉ በሙሉ በእጁ ያደረገው ወያኔ ሀላፊነት በጎደለው የጭካኔ ተግባር በአማራው ህዝብ ላይ ሽብር ነዛ- ሞት አወጀ:: መዐሕድን በሁለት እግሩ እንዲቆም ለማድረግ በሰውሀይል ማጠናከር ያስፈልጋል:: ህዝብን የማደራጀትና የማንቃት ስራ ገንዘብ ያስፈልገዋል:: የወገን ጩኸት ያባነናቸው አማሮች በከተሞች አካባቢ በቁጭት ድርጅቱን ለማጠናከር ደፋ ቀና ማለት ጀመሩ::

ብዙሀኑ ገበሬ ምን እየተደረገ እንደሆነ እንኳ አያውቅም:: መንግስት ይመጣል መንግስት ይሄዳል:: “ሽህ ቢታለብ ያው በገሌ” እንዳለችው ድመት ማንም መጣ ማን ያው አርሶ አደር ነውና ሁሉም የእለት ጉርሱን የአመት ልብሱን ያሟላ ዘንድ ደፋ ቀና ይላል:: ሌሊት ወጥቶ ሌሊት ይገባል:: ጠብ ለማይል ኑሮ ነጋ ጠባ ደፋ ቀና እንዳለ ይኖራል:: ወሬ የሚያዳምጥበት ጊዜ የለውም:: ብቻ ይሰራል- ሰርቶ ከሚያገኘው ይገብራል:: ገበሬው የሚፈቀደው የግብር ጊዜ ወይም የተለየ መዋጮ እንዲያደርግ ሲፈለግ: አሊያም ለውትድርና:: ከዚያ ውጭ የት ወደቀ የሚለው የለም:: እርሱም የቤቱን ገበና ለመሸፈን ላይ ታች ከማለት ውጪ ስለፖለቲካ የሚያውቀው ነገር የለውም:: መንግስት- አስተዳዳሪ: የህዝብን ሰላም የሀገርን ዳር ድንበር አስጠባቂ: መሰረት ልማት (መንገድ: አስኳላ ትምህርት: የጤና ተቋም…) አስፋፊ መሆኑን ያውቃል::  የመንግስት ዘር መኖሩን ግን አያውቅም:: አንዱን ህዝብ ጎድቶ ሌላውን ለመጥቀም እንደሚያልምም አያውቅም:: በርግጥ በዘር ወይም በቀረቤታ የሚሰሩ ባለስልጣኖች እንደነበሩ: አሁንም እንደማይጠፉ ያውቃል:: የማያውቀው ነገር ቢኖር መንግስት ለአንዱ ወላጅ አባት ለሌላው ደግሞ የእንጀራ አባት መሆን ስለመቻሉ ነው::

 

ከተሜው የገበሬውን ያህል ለፖለቲካ ሩቅ አይደለም:: ለሚዲያወች የተሻለ ቀረቤታ ስላለው ምን እየተካሄደ እንዳለ መጠነኛም ቢሆን ግንዛቤው አለው:: ስለዚህ ይህንን የህብረተሰብ ክፍል ማደራጀት ብዙም አይከብድም:: ግን እንዴት? ሰላምና መረጋጋት ብሎ መንግስት ያደራጃቸውና የኮር አባል ተብለው የሚታወቁት ምልምል ካድሬወች ህዝቡን ሰላሙን ነሱት:: በኮር አባላት ስብሰባ ላይ የመጀመሪያው ክፍል ኢንፎርሜሽን ማቀበል ነው:: ስለዚህ የኮር አባላቱ አይደለም የሚወራውን የሚበላውንና የሚጠጣውን ሳይቀር እያነሱ እገሌ እንዲህ አለ: እገሊት ከገሊት ቤት ቡና ጠጣች በማለት በየተሰጣቸው ቀጠና ያዩትንና የሰሙትን እያጋነኑ ያቀርቡ ጀመር:: ኢንፎርሜሽን ያላመጣ የኮር አባል ስለሚገመገም ግምገማውን ለማለፍ አይደለም የታየውና የተሰማው ያልታየና ያልተደረገው ሁሉ በንጹሀን ላይ መወራት ጀመረ:: የኮር አባላቱ በግላጭ አይታወቁ ስለነበር አንዱ አንዱን ማመን እየከበደው መጣ:: ፍርሀትና ጥርጣሬ ነገሰ:: የመንግስትን ፖሊሲ ይነቅፋሉ የተባሉ ሰዎች የተነፈሱት ሳይቀር እየተነገራቸው ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ምክርና ማስፈራሪ ይሰጣቸው ጀመር:: ምክርና ማስጠንቀቂያውን የጣሱ ሰዎች ሰርቀው ሊያመልጡ ሲሉ ተገደሉ: ወይም መጠጥ ቤት በተነሳ ግጭት ክፉኛ ተደብድበው ሞቱ: ወይም ባላንጣ ጊዜ ጠብቆ ገደላቸው እየተባሉ ተወገዱ:: የደርግ የቀይ ሽብር በድብቅ መተግበር ጀመረ:: ይህን ዘመን ለማለፍ ከተሜው ኮረንቲና ፖለቲካን በሩቁ አለ::

 

ድርጅት ለመመስረት የሚደረገው ትግል ግን በምንም መልኩ ሊደናቀፍ አይችልም:: መከፈል የሚያስፈልገው መስዋእትነት ተከፍሎ መዐሕድ እውን መሆን አለበት:: ድርጅቱ ስር እስኪሰድ ድረስ ለየት ያለ አካሄድ መከተል እንደሚገባ በመታመኑ በአንዳንድ አካባቢ ዱሮ በኢሕአፓ ጊዜ በነበረው የአደረጃጀት ስርአት መሰረት እምነት የሚጣልባቸውን በተለይ ደግሞ በዚህ መንግስት ደስተኛ ያልሆኑትን ሰዎች ሁለትና ሶስት በአንድ ላይ በማደራጀት ግንዛቤ ማስጨበጥና የአባልነት ፎርም ማስሞላት ተጀመረ:: በዚህ መልክ ውስጥ ውስጡን መዐሕድ ስር መስደድ ጀመረ:: በርግጥ የመጣውን ሁሉ በጸጋ ለመቀበል የግንባር ስጋ ሆነው ፈጥጠው የወጡ በርካታ ሰዎች ነበሩ:: መዐሕድ የሰላም ታጋይ ድርጅት ነው:: ሰላማዊ ትግል ማለት ቅሬታን ሰላማዊ በሆነ መንገድ መግለጽ ማለት ነው:: ቅሬታ መፍትሄ ካላስገኘ ትግሉ በመንፈስና በአካል እስከመሸፈት ያደርሳል:: ይህም ማለት ከሀይል ርምጃ በመለስ ያሉትን ሁሉ መጠቀም: እምቢ አልታዘዝም አላደርግም በማለት ተቃውሞን መግለጽን ያጠቃልላል:: አዎ! ሰላማዊ ትግል ማለት ከመንግስት በኩል የሚሰነዘረውን ማንኛውም ጥቃት በሰላም መቀበል ማለት ነው:: ሳያቆስሉና ሳይገድሉ እየቆሰሉና እየሞቱ ማሸነፍ ማለት ነው:: ይህ የትግል ባህሪ በለየላቸው የወያኔ አይነት አምባገነን መንግስታት ዘንድ በእጅጉ ጎጅ ነው:: የህዝብ እምቢ ማለት አያስደነግጣቸውም:: ራሳቸውን መለስ ብለው ለመመርመር አያስችላቸውም:: ይልቁኑ በተደፈርኩ መንፈስ ያወራጫቸዋል:: ለበቀል ጦራቸውን ይሰብቁና ያገኙትን ሁሉ ማጥቃት ይጀምራሉ:: በዚህ መልኩ ሰላማዊ ትግል መስዋእትነቱን ያከፋዋል:: ኋላቀር በሆኑ አምባገነኖች በሚመሯቸው አገሮች ዘንድ ሰላማዊ ትግል የሽምቅ ውጊያ ያህል ያስቀጣል:: ሰላማዊ ታጋይ ማለት ለመንግስት አመራር አልመችም የሚል አጉራ ዘለል ነውና የሸማቂውን ያህል ይቀጣል:: አምባገነኖች አይደለም የተቃወማቸውን ኮከባቸው ያልፈቀደውን ሰው ሁሉ ቢገሉ ይችላሉ:: ወያኔወች ደግሞ ሰላማዊ ታጋይ ያውም የአማራ ማየት ቀርቶ መስማትም አይፈልጉም:: ሆኖም በአግባቡ ከተጠቀሙበት ሰላማዊ ትግል በአጭር ጊዜ ውጤታማ ያደርጋል:: ውጤታማነት ከጠንካራ አደረጃጀትና ከበሳል አመራር ውጭ አይገኝም:: መዐሕድ አመሰራረቱ ለፖለቲካ የስልጣን ፉክክር አይደለም:: አላማው በአማራው ላይ እየደረሰ ያለውን ዘርፈ ብዙ ጭቆናና ግድያ ለአለም መንግስታትና ለሰብአዊ ድርጅቶች ለማሰማት ነው:: ግን ሁሉም ትግል ያስፈልገዋል:: በዚህ ሂደት ወያኔ መራሹ መንግስት መውደቅ ከቻለ እሰየው ነው- በደምና በአጥንት የሚያምኑት እኩዮች ከጠፉ አማራውን ለይቶ የሚያሳድድ አይኖርም ማለት ነው:: ከዚያ በኋላ ለኢትዮጵያ የሚበጅ የህዝብ አስተዳደር ለመመስረት ተፎካካሪ ሆኖ መቅረብ ይቻላል:: ለሁሉም የህዝብን መንፈስ መማረክ የሚያስችል ሁለንተናዊ ብቃት መጎናጸፍ ያስፈልጋል::

 

የልጆች ማስፈራሪያ “አባ ዳውሎ” ተብሎ ይጠራል:: አባ ዳውሎን አይቶ የሚያውቅ ልጅ የለም:: ግን አባ ዳውሎን ይፈራል:: ሲያለቅስ የነበረን ልጅ “አባ ዳውሎ መጣብህ” ካሉት ልቅሶውን ይውጣል:: ሻእቢያና ወያኔ ደግሞ ብሄር ብሄረሰቦችንና ህዝቦችን የሚያስፈራሩት “አማራ መጣልህ” ብለው ነው:: በሻእቢያና በወያኔ የተሰበከ የዋህ ይህንን ተቀብሎ አስተጋብቷል:: በኤርትራ እናቶች ልጆቻቸው ሲያስቸግሯቸው “አማራ መጣልህ” ይሏቸው ነበር:: አማራ አፉ እንደአዞ አፍ 180 ዲግሪ የሚዘረጋ ጆሮው እንደዝሆን የሰፋ: አስፈሪ የሆነ ፍጡር እንደሆነ ተደርጎ እየተነገራቸው ያደጉት ልጆች ታዲያ አማራ መጣብህ ሲባሉ ቱር ብለው የትም ይጠፋሉ- እናቶችም ከህጻናቱ ብጥበጣ ተንፈስ ይላሉ:: ይህ በኤርትራ የልጆች ማስፈራሪያ የነበረው አማራ አሁን ከልጆች አልፎ የብሄር ብሄረሰቦች ማስፈራሪያ ሆኗል:: “ነፍጠኛ” የአማራ ተለዋጭ ስም ነው:: እና ነፍጠኞች ከተባለ አማሮች ማለት ነው:: “ነፍጠኞች የብሄር ብሄረሰቦች ጠላቶች ናቸው- ኢትዮጵያ ደግሞ እስር ቤታቸው:: ነፍጠኞች አንገታቸውን ቀና ሊያደርጉ አይገባም:: አንገታቸውን ቀና ካደረጉ መሬትህን ይወስዳሉ: ነጻነትህን ይነጥቃሉ” ነቅተህ ጠብቅ ተብለው ይቀሰቀሳሉ:: የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች አማሮችን ጠንቅቀው ያውቋቸዋል:: አማሮች በያሉበት ላባቸውን አንጠፍጥፈው ሰርተው የሚኖሩ እንደሆኑ አሳምረው ያውቃሉ:: አሁን አማራ ክልል ተብሎ በሚታወቀው ክልል የሚኖሩ አማሮችም ቢሆኑ የእግር ጫማ እንኳ የሌላቸው ለፍቶ አዳሪወች መሆናቸውን ይረዳሉ:: አማሮች ጠላቶቻችሁ ናቸው ሲባሉ ግራ ተጋብተዋል:: የትኞች አማሮች ናቸው የእኛ ጠላቶች ብለው መጠየቅ አይችሉም:: እንዲህ ያለ ሰው “የነፍጠኛ ሎሌ” ሊባል ይችላል:: አማሮች በየቦታው ሲታደኑ ብሄር ብሄረሰቦች ውስጣቸው በሀዘን ተኮማትሯል:: በየቦታው ተበትነው ባሉት አማሮች ላይ ጥቃት ለመፈጸም በወያኔና በአጋሮቹ ከተዘጋጁት ገዳይ ስኳዶች ግን ሊታደጓቸው አልቻሉም:: እና የብሄር ብሄረሰቦች አባ ዳውሎ (አማራ) ዘሩ እንዳይጠፋ ተደራጅቶ ድምጽን ከፍ አድርጎ መጮህ: ቀሪውን ወንድም ኢትዮጵያዊ ሀቁን ማስጨበጥና የትግል አጋር ማድረግ ያስፈልጋል::

 

ሻለቃ ሀይለየሱስ በባህርዳር ልዩ ዞንና በምእራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ሀላፊነት ተጥሎባቸዋል:: አባላትን መመልመል: ማደራጀት: የአባላት መዋጮ ማሰባሰብና ቢሮ መክፈት ይኖርባቸዋል:: ሰው የመቅረብ ልዩ ችሎታቸው ወሳኝ የሆኑ ሰዎችን ለማግኘት ረድቷቸዋል:: በጥቂት ወራቶች ውስጥ ምእራብ ጎጃምን እስከቀበሌ ድረስ ወርደው ማደራጀት ቻሉ:: ቢሮወች በበርካታ የወረዳ ከተሞች ተከፈቱ:: ቀስ በቀስ የህቡእ እንቅስቃሴው ገሀድ መውጣት ጀመረ:: የባህር ዳር ቢሮ በማእከልነት ያገለግል ጀመር:: ምንም እንኳ ሀይለየሱስ የምእራብ ጎጃምና የባህርዳር ልዩ ዞን አስተባባሪ ቢሆኑም በክልሉ ዋና ከተማ ተቀማጭ ስለሆኑ የአማራውን ችግር ከየዞኖች እየተቀበሉ ለበላይ የማሳወቅ ስራ በመስራት: መግለጫ በማውጣትና ህዝባዊ ስብሰባወችን በማካሄድ ግዙፍ ስራ ሰርተዋል:: በሰሜን ጎንደር: በደቡብ ጎንደር: በአዊና በምስራቅ ጎጃም ዞኖች ከአቶ አባይነህ ብርሀኑ ጋር በመሆን የዞን አስተባባሪወችን መልምለዋል- ቢሮወችን ከፍተዋል::

 

የት ይደርሳሉ ብለው በንቀት ይመለከቷቸው የነበሩ የየደረጃው የወያኔ አንጋቾች ህዝቡ ቀስ በቀስ ከእጃቸው እያፈተለከ ወደ መዐሕድ እቅፍ መሰባሰቡን ሲያዩ መበራገግ ጀመሩ:: በሻለቃ ላይ ፈተናወች በዙ:: መጀመሪያ ምክር ቢጤ ተሰጣቸው:: “ምንህ ተነካ- ለምን አርፈህ አትቀመጥም” ተባሉ:: ቀጠሉ የወያኔ ተስፈኞች- ” ብታርፍ ይሻልሀል:: አሊያ አወዳደቅህ ይከፋል” አሏቸው:: አልገባቸውም እንጅ ሀይለየሱስ አይደለም ለዛቻ ለጥይትም አይንበረከኩ:: ይህን ትግል ሲቀላቀሉ ብዙ ነገር ሊደርስባቸው እንደሚችል ተረድተው ነው የወሰኑት:: እና ሀይለየሱስ ይበልጥ ቀበቷቸውን ጠበቅ አድርገው ህዝብ የማደራጀቱን ስራ ገፉበት:: ፖሊሶችና የደህንነት ሀይሎች በየሄዱበት ይከታተሏቸዋል:: ሻለቃ ክፉ አይወጣቸውም:: ብቻ “እንዲያው ልፉ ብሏችሁ እኮ ነው” ይላሉ: ምንም ስህተት እንደማይገኝባቸው ለመግለጽ::

 

“ማሸማቀቅ” የወያኔ አንዱ የትግል ስልት ነው:: አንድ ሰው ከሚፈጽመው ተግባር እንዲታቀብ ለማድረግ ሲፈለግ በስብሰባ ላይ የማስደንገጥ: በፖሊስና በደህንነት ክትትል የማስበርገግ ድርጊት ነው- ማሸማቀቅ:: ይህ ግን ሀይለየሱስ ዘንድ ሊሰራ አልቻለም:: ራሳቸው ሀይለየሱስም ሆኑ ቤተሰቦቻቸው በሌሉበት ቤታቸው በተደጋጋሚ ተፈትሿል:: ምን ይገኝባቸዋል? ምንም:: እርሳቸው እንደሆኑ የሰላም አርበኛ::

 

ወያኔ መዐሕድን ለማጥቃት ሲንቀሳቀስ ብአዴኖች ግዳይ ጥለው ሊሾሙ ሊሸለሙ ተቁነጠነጡ:: በወቅቱ የተከሰቱ ችግሮች ሁሉ የመዐሕድ አፍራሽ እንቅስቃሴ ውጤቶች ተደርገው በመንግስት ሜዲያወች ይናፈሱ ጀመር:: መዐሕድ “ካለወቅቱ የመጣው ዝናብ በእኛ እንዳይሳበብ እየሰጋን ነው” ሲል ወያኔ እየፈጠረበት ያለውን ልብ ወለድ ክስ ነቀፈ:: ወያኔ ግን ሰቅጠጥም አላለ:: ይባስ ብሎ በፈጠራ ክስ የድርጅቱን መስራችና የአማራ ጠበቃ የነበሩትን ፕሮፌሰር አስራት ወ/የስን አሰረ:: የወያኔ አላማ መሪው ከጨዋታ ውጪ ከሆነ ተከታዩ ይበተናል የሚል የተሳሳተ አላማ ነበር:: ያ ዱሮ ቀረ:: ዱሮ የጦር መሪ ሲሞት ሰራዊቱ ትጥቁን ይፈታ ነበር አሉ:: “ንጉስህ ወይም መሪህ ተማርኳልና እጅህን ስጥ” ተብሎ ይለፈፋል:: በቃ በዚያው ጦርነቱ ያበቃል:: ያ ጊዜ አሁን አይደለም:: ሰላማዊ ፍልሚያው ይበልጥ ተጧጡፏል:: አባላት ይመዘገባሉ: ቢሮወች ይከፈታሉ: የፖለቲካ ትምህርት ይሰጣል::

 

የመዐሕድ ጩኸት ፍሬ አሳየ:: አማሮችን በአማራነታቸው ብቻ ሰብስቦ መግደል ጋብ አለ:: ስለዚህ አሁን መዐሕድ ከአማራው አልፎ ለመላው ኢትዮጵያዊ ሊቆም የግድ ይላል የሚሉ ወገኖች ተበራከቱ:: እውነት ነው:: መጀመሪያምኮ ቢሆን መዐሕድ የተመሰረተው አማራ ተኮር የሆነ ግድያ በመስፋፋቱ ብቻ ነው:: ይህ ችግር ተንፈስ ካለ የሚቀጥለው ተግባር በኢትዮጵያ ላይ በጉልበቱ ነግሦ በዘርና በቋንቋ ህዝቡን እየከፋፈለ ያለውን ጸረ ህዝብና ጸረ ኢትዮጵያዊ ድርጅት ከኢትዮጵያውያን ጫንቃ ላይ አሽቀንሮ መጣል ይሆናል:: ይህ ውጤት ሊመጣ የሚችለው መላው ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ ተሰባስበው ለአንድ አላማ መሰለፍ ሲችሉ ብቻ ነው:: መዐሕድ ግቡን አሳክቷል:: ቀጣዩ ትግል ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በእኩልነት የሚያሳትፍ ድርጅት መስርቶ በዚያው የሚካሄድ ይሆናል:: በዚህ መልኩ መኢአድ ተመሰረተ::

 

ሻለቃ ሀይለየሱስ እጅጉ ኢትዮጵያዊ ወታደር ነበሩ:: ሲያደሙና ሲደሙ የነበሩት ለሀገራቸውና ለህዝባቸው ነው:: ሀገራቸው ኢትዮጵያ ህዝባቸውም ኢትዮጵያውያን ናቸው:: ቀዳሚ አላማቸውን ከመዐሕድ ጋር ያሳኩት ሀይለየሱስ ለቀጣይ ግዳጅ ከመኢአድ ጋር ተሰለፉ::

 

ይቀጥላል

 

 

ጠ/ቤተ ክህነት የመምህር ግርማ ወንድሙን እገዳ አጸና

$
0
0

girma1 ዘ-ሐበሻ ከጥቂት ሳምንታት በፊት መምህር ግርማ ወንድሙ በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ እንዳያጠምቁ መታገዳቸውን መዘገቧ ይታወሳል። ዛሬ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዜና እንደሚያመለክተው ደግሞ አዲስ አበባ የሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት የአጥማቂውን እግድ እንዳጸና ገልጿል። በአነጋጋሪነታቸው የቀጠሉት መምህር ግርማ እንዳያጠምቁ መታገዳቸው ከተሰማ በኋላ ም ዕመናን የተለያዩ አስተያየቶችን ሲሰነዝሩ ቆይተዋል።
ጠ/ቤተክህነቱ ግንቦት 2 ቀን 2005 ለ:-
በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ ሲያጠምቁ የከረሙት አነጋጋሪው መ/ር ግርማ ወንድሙ እንዳያጠምቁ ታገዱ- ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት
- ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ ልዩ ጽ/ቤት
- ለአስተዳደር መምሪያ
- ለሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
- ለምሥራቅ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት
- ለፌዴራል ጉዳዮች ጽ/ቤት
- ለፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን
- ለብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት
- ለአ/አ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን
- ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ
- ለአ/አ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ
- ለቂርቆስ ክ/ከ ፍትሕ ጽ/ቤት
ግልባጭ አድርጎ በጻፈው የእግዳ ማጽኛ ደብዳቤ ላይ መምህሩን “አጥማቂ ነኝ ባይ” ሲል ገልጿቸዋል። ደብዳቤውን እንደወረደ ያንብቡት።

ጉዳዩ፡- በአስቸኳይ አጥማቂ መምህር ግርማ ወንድሙ በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ሰ/ጉ/ጽ/ቤት በቁጥር 339/ቀ/አ/ቤ/ክ በ28/8/2005 ዓ.ም የተሰጠው እገዳ መ/ፓ/ጠ/ጽ/ቤት ያጸናው ስለመኾኑ ይመለከታል፤

መ/ር ግርማ ወንድሙ ሰባኬ ወንጌልና አጥማቂ ነኝ፤ የማዳን ፈውስ አለኝ በማለት በሕገ ወጥ መንገድ እስከ አሁን ድረስ በደብሩ እያጠመቁ ይገኛሉ፡፡

ይኹንና በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ከ1993 ዓ.ም እስከ 2002 ዓ.ም ድረስ በየወቅቱ በሕገ ወጥ መንገድ የማዳን ፈውስ አለኝ በማለት ሕዝበ ክርስቲያኑን በየደብሩ ቅጽር ግቢ በማሰባሰብ የሚያጠምቁትን በተመለከተ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

ከቤተ ክርስቲያኗ ቀኖና ሥርዐት ውጭ በሚፈጸም ስብከትና ጥምቀት፤
የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ሳይፈቅዱ የሚሰጥ የወንጌልና ጥምቀት አገልግሎት መስጠትን በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነ ቢኾንም በሥርዐተ አልበኝነት በተለያዩ ቦታዎች የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሲጣስ ይታያል፡፡
በመኾኑም መምህር ግርማ ወንድሙ በደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በሕገ ወጥ መንገድ የሚፈጽሙት ሕገ ወጥ የማጥመቅ ሥርዐትና የወንጌል አገልግሎት መኾኑን እየገለጽን የእምነታችን ተከታይ ሕዝበ ክርስቲያኑ ከዚህ እግድ ጋራ በተያያዘ የጸጥታ ችግር እንዳይገጥመው የሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት ጥብቅ ክትትል በማድረግ ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርግ እያሳሰብን የሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ አካላትም የቤተ ክርስቲያኒቱን ውሳኔ ተግባራዊ በማድረግ ረገድ አስፈላጊው ትብብር እንዲያደርጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን::

የመምህራን ማኅበር በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችና ተቋማት መዳከም ዙሪያ ስጋቱን የሚገልጽ መግለጫ አወጣ

$
0
0

ethiopian teachers
(ዘ-ሐበሻ) በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ “የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆችና ተቋማት” የውድቀት አደጋ አንዣቦባቸዋል ሲል ስጋቱን ገለጸ። ማህበሩ ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫው “በመምህራን ላይ የሚታየው የ እውቀትና የክህሎት ክፍተት ለመሙላት አጫጭር ስልጠናዎችንና የክረምት ኮርሶች ቢሰጡም የትምህርቱ ጥራት ዋነኛ መመዘኛ መስፈርት የፖለቲካ ታማኝነት የሚለው ስንኩል የወያኔ አስተሳሰብ ገኖ በመውጣቱ በርካታ ልምድ ያላቸው መምህራን ሥራቸውን እያለቀቁ መሄዳቸው የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችና ተቋማት በአሁኑ ጊዜ ይበልጥ ተዳክመዋል” ብሏል።

Download (PDF, 621KB)

ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ በጀርመን በርሊን ከተማ ተካሄደ

$
0
0

ዘጋቢ በየነ መስፍን ከጀርመን

እ.ኤ.አ በሜይ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በጀርመን በርሊን ከተማ የኢትዮጵያውያን የፖለቲካና ሲቪክ ማህበር አባላት አንድነት ድርጅት (ኢ.ፕ.ኮ.) በጠራው ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከተለያዩ የጀርመን ከተሞች የተሰባሰቡ ቁጥራቸው ከ350 በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያን፣ትውልደ-ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የተገኙ ሲሆን የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ፓርቲ /ኢሕአፓ/፣የሞረሽ ወገኔ የአማራ ድርጅት /ሞረሽ/ እና የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር አመራር እና አባላትም በሰልፉ ላይ ተገኝተዋል።
germeney demonstation ethiopians
መነሻውን ”ቬንደርሸር ማርክት አንድ” /Werderscher Markt 1/ ከሚባለው የከተማው ክፍል በማድረግ በተለያዩ መፈክሮችና የኢትዮጵያ ባንድራ በማሸብረቅ ጉዞውን ወደ ቻንስለር አንጌላ ሜርክል ጽ/ቤት አድርጓል።
”በአማራ ህዝብ ላይ የሚደረገው የዘር ማጥራት ዘመቻ ይቁም!”
”የህሊና እስረኞች ይፈቱ!”
”የሃይማኖት ነፃነት ይከበር!”
”ከአባይ በፊት ዘረኝነት ይገደብ!”
”የጀርመን መንግስትና የአውሮፓ ህብረት ለአፋኙ የወያኔ አገዛዝ የሚያደርጉትን የገንዘብ ድጋፍ ያቁሙ!”
”ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ይከበር!” የሚሉ መፈክሮች በሰፊው የተደመጡ ሲሆን ከአንድ ሰዓት ተኩል የእግር ጉዞ በኋላ ተሰላፊው በመጀመሪያ በጀርመን ፓርላማ /Bundestag/ ፊት ለፊት በኋላም በጀርመን ቻንስለር ጽ/ቤት ፊት ለፊት በመሰባሰብ የተለያዩ መፈክሮችን ያሰማ ሲሆን ከአንድ ወር በፊት በኢ.ፕ.ኮ. አማካኝነት በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰውን የዘር ማጥራት ወንጀል የሚቃወሙ ቁጥራቸው ከሶስት ሺህ በላይ የሚሆኑ ጀርመናውያንን ፊርማ የያዘውን ሰነድ ለቻንስለሯ ጽ/ቤት ገቢ የተደረገ ሲሆን የኢ.ፕ.ኮ. ሊቀ መንበር፣እንዲሁም የኢሕአፓ ተወካይ፣የሞረሽ እና የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ተወካዮች አጠር ያለ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ይህ ከሶስት ሰዓት በላይ የፈጀ የተቃውሞ ሰልፍ በሠላምና በታላቅ ድምቀት ተጠናቋል።

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live