Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ብአዴን ማን ነው? (ገብረመድህን አርአያ፣ አውስትራሊያ)

$
0
0

(ገብረመድህን አረአያ ከፐርዝ አውስትራሊያ)

(ገብረመድህን አረአያ ከፐርዝ አውስትራሊያ)

የአንድን ድርጅት ማንነቱን ከማቅረብ በፊት ቀደም ብሎ የተፈጸመውን ስህተት፣ ቀጥሎም ኢህአፓን ለማጥፋት በህወሓት እና በሻእቢያ የደረሰበትን ጥቃት አጠር ባለ መልኩ ማቅረብ አስፈላጊ ይሆናል።
የስትራተረጂ ስህተት ለከባድ ወድቀት ይዳርጋል።

ኢህአፓ ትግሉን የጀመረው ገና በ1960 መጀመሪያ ነበር። አብዮቱ እየተቀጣጠለ ሃገር አቀፍ ሆነ። ዘውዳዊ ስርዓት ወድቆ በማርክሲዝም ሌኒኒዝም ርእዮተ ዓለም የሚመራ ሶሻሊዝም የኢትዮጵያ ስርአት እንዲሆን ነበር። ይህ ግራ አክራሪ ስታሊኒዝም በቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቨርሲቲ ይማሩ በነበሩ የተሰባሰበ ቡድን፣ የወቅቱ አብዮተኞች ተገቢውን መልክ የያዘ አደረጃጀት ያልነበረው፣ አብዮተኛ የሚል ስም በማግኘታቸው ብቻ “ዲሞክራሲያ” ተብሎ የሚታወቀውን የኢህአፓ ልሳን በየሳምንቱ በመበተን አሁን ኢትዮጵያ የደረሰባትና እየደረሰባት ያለው ከባድ ችግር የከፈተው እነ ዋለልኝ መኮንን እና የኢህአፓ ግብረአበሮቹ የስታሊን ደቀ መዛሙርት ኢትዮጵያን አደጋ ወስጥ ጣሏት። በዚህ ወቅት ሰፊውን ትኩረት የሰጡት፤

1. በኤርትራ ጥቅያቄ ላይ ኢህአፓ ያለው አቋም ኤርትራ ከዚህ ቅኝ አገዛዝ ነፃ በመሆን ተገንጥላ ነፃ መንግሥት ማቋቋም ሙሉ መብቷ መሆኑን ያምናል፤

2. ኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦች ወህኒ ቤት እንደመሆኗ የኢህአፓ አቋም በዚሁ ጥያቄ ላይ ርቱእና ግልጽ ሲሆን፣ ብሄር ብሄረሰቦች የራሳቸውን እድል በራሳቸው በመወሰን እስከ መገንጠል መብታቸው ያልተገደበ ነው ይላል።

ይህ ትንታኔ ማንም ኢትዮጵያዊ በተጨማሪ ለማረጋገጥ ክፈለገ “ዲሞክራሲያ” ቅጽ 8 ቁጥር 1፣ የካቲት 23 ቀን 1973 የታተመውን ሙሉ ሃሳቡን በድጋሚ ጽፎታል፣ የቃላት ለውጥ በትንሹ ቢኖርበትም። ይህንን ጽሑፍ ለማግኘት EPRP በሚለው ድረገጽ በመግባት የዲሞክራሲያን እትም ከ1961 እስከ ዛሬ የሚለውን ፈልጋችሁ አንብቡ። ይህ ጽሑፍ የሚያሳዝነው ኢህአፓ አሲምባ እንደገባ ታጋዮቹ በፈጠሩት ጫና በሻእቢያ 1ኛ ጉባኤ 1969 መጨረሻ የአቋም ለውጥ በማድረግ ኤርትራ የኢትዮጵያ አካል ናት፤ የኤርትራ ጥያቄ የዲሞክራሲ ጥያቄ በመሆኑ ትግሉ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ትግል ስለሆነ ኤርትራም የዚሁ አካል እንጂ ቅኝ ተገዢ አይደለችም በማለት በጉባኤው የሰጠው ውሳኔ ቅጥረኛው ህወሓት ታህሳስ 1972 የኢህአፓ ተዋጊ ክንፍ ሰራዊት ከባድ መስዋእትነት ክፍሎ በወያኔ ተደመሰሰ። በውጭ ሃገር የሚኖሩ የኢህአፓ አመራር በየካቲ 1973 በዲሞክራሲያ ልሳን ያወጡት ጽሑፍ የኢህአፓው ተዋጊ ክንፍ ኢህአሠ ታጋይ ለናት ሃገሩ ኢትዮጵያ የከፈለውን መስዋእትነት ውድቅ ለማድረግ የታቀደ ነው፤ ለምን?

ከላይ የተጠቀሱት ሁለት ነጥቦች የኢህፓ አመራር በዲሞክራሲያ ልሳኑ ደጋግሞ በመዘርዘር ጠባቦችና ጸረ ኢትዮጵያ አንድነትና ሉአላዊነት ሃይሎች እንዲፈጠሩ አደረገ።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ


የኃይለማርያም ደሳለኝ ቁልቁለቶች –ከተመሰገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)

$
0
0
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

በ2005 ዓ.ም መጀመሪያ አቶ ኃይለማርያም “ጠቅላይ ሚኒስትር” ተደርጎ በኢህአዴግ ሲሾም፤ በፓርቲው ውስጥ አክራሪ ብሔርተኛ የአመራር አባላት ከመኖራቸው አኳያ፤ መቼም ቢሆን “ራሱን ችሎ ይቆማል” ብሎ መጠበቁ ተምኔት እንደሆነ በርካታ የፖለቲካ ተንታኞች መናገራቸው ይታወሳል፡፡ ይህ ኃይል እንኳን እንደ ኃይለማርያም ላለ የድል አጥቢያ መሪ ቀርቶ፣ ከድርጅቱ ምስረታ ጀምሮ እስከ ምኒሊክ ቤተ-መንግስትም ድረስ ታላቅ የተጋድሎ ታሪክ ለነበረው አቶ መለስም ቢሆን ክፍተት ካገኘ አለመመለሱን የ93ቱ ሣልሳዊ ህንፍሽፍሽ በግልፅ አሳይቶ ማለፉ አይዘነጋም፡፡ በተጨማሪም ራሱ መለስ ዜናዊ በድህረ ምርጫ 97 የተፈጠረውን አለመግባባት ተከትሎ ዘብጥያ ወርደው የነበሩትን የቅንጅት አመራሮች “ከእስር እንዲፈቱ ብፈልግም አክራሪው ኃይል ተቃወመኝ” ማለቱን ዊክሊክስ የተሰኘው የመረጃ መረብ የአሜሪካ አምባሳደርን ጠቅሶ ይፋ ማድረጉ ይህንኑ ያስረግጣል፡፡ የአምባሳደሩ መረጃ የተጋነነ፤ አሊያም “ተጋግሮ የቀረበለት ነው” ሊባል ቢችል እንኳ “ጭስ በሌለበት…” እንዲሉ፤ በግንባሩ ውስጥ አክራሪ ኃይል ለመኖሩ በጠቋሚነት ሊወሰድ ይችላል፡፡Temesgen Desalegn “Fact” Ethiopian Amharic newspaper editor

ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ መለስን ከተካበት ዕለት አንስቶ፣ ያደረጋቸው ዲስኩሮችም ሆኑ ለቀረቡለት ጥያቄ የሰጣቸው ምላሾች በአክራሪው ኃይል ተጽእኖ ሥር ማደሩን ያሳያል፡፡ የድርጅቱ የታሪክ ንባብም ቢሆን፣ በአቅመ ደካማ የመጠቀም የፖለቲካ ጨዋታው የሰነበተ መሆኑን ያመላክታል፡፡ ኃይለማርያም ከሹመቱ በኋላ ከባሕሪው አፈንግጦ፣ ዝነኛዋን የመለስ ዜናዊን ሕዝባዊ ሽብር መፍጠሪያ ‹‹ቀይ መስመር››ን፤ ‹‹እሳት መጨበጥ›› በሚል ተክቶ የተቃውሞ እንቅስቃሴን በሙሉ እስከማስፈራራት መገፋቱም የዚሁ ውጤት ይመስለኛል። በተቀረ እርሱ ወደ ሥልጣን በመጣበት መጀመሪያ አካባቢ፣ ‹‹ኃይማኖተኛ››ነቱን ብቻ በመጥቀስ ‹‹ቤቴን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት›› በሚል ሥርዓታዊ ማፍያነትን ባደራጁ ጓደኞቹ ላይ ጅራፍ እስከማወናጨፍ ይደርሳል ተብሎ መገመቱ፣ በግንባሩ ውስጥ የተንሰራፋውን አክራሪ ኃይል በቅጡ ካለመረዳት የመነጨ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ እዚህ ጋ ሳይጠቅስ የማይታለፈው ጥቅምት 10 ቀን 2005 ዓ.ም የወጣው ‹‹ሪፖርተር ጋዜጣ›› በልዩ እትሙ፣ ኃይለማርያም ‹‹ቄስ›› ተብሎ ሊቀባ አንድ ወር ሲቀረው በትምህርት ምክንያት ከሀገር እንደወጣ ካስነበበበት ጋር የሚያያዘው ነው፡፡ ወደ ፖለቲካው ከመቀላቀሉ በፊት የሚያመልክበትን ‹‹የኢትዮጵያ ሐዋርያት ቤተክርስቲያን›› ቄስ ህዝቅኤል ጎዴቦን ‹‹ፖለቲካ ውስጥ መግባት ሀጢአት አይሆንብኝምን?›› ሲል መጠየቁን ጋዜጣው አትቷል፡፡ ግና፣ ምን ዋጋ አለው? ባልተጠበቀ ፍጥነት ከተራ ፖለቲከኝነት አልፎ የሀገሪቱ መሪ ለመሆን በመብቃቱ፣ ‹‹ቅስና››ው በመንገድ ሊቀር ተገደደ እንጂ፡፡ እርሱም ቢሆን ዛሬ እንዲህ አይነት ጥያቄ አያነሳም፤ በፈሪሃ እግዚአብሔሩም ቦታ፣ ፈሪሃ ኢህአዴግ ተተክቷል፡፡ እናም ከእስልምና መንፈሳዊ መሪዎች እስከ ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ያሉ ንፁሀን፣ በራሱ አነጋገር ‹‹እሳት በመጨበጣቸው›› ወደ ‹‹ቃሊቲ›› ተላልፈው ምድራዊውን ገሀነም ይቀበሉ ዘንድ ቡራኬ ሰጥቷል፡፡ Dead end - Copy ሰሞነኛው ጉዳይ

አቶ ኃይለማርያም በስድስት ወር (በጥር) ለተወካዮች ም/ቤት ማቅረብ የነበረበትን ሪፖርት በዘጠኝ ወሩ ባለፈው ሳምንት ባቀረበበት ወቅት፣ ከምርጫው በፊት የፖለቲካ ማሻሻያ መጠበቁ የዋህነት እንደሆነ የጠቆመን፣ የም/ቤቱ አባል አቶ ግርማ ሰይፉ የጠበበው ምህዳርን አስመልክቶ ላቀረበለት ጥያቄ ‹‹ዲሞክራሲ በአንድ ሳምንት ተበጥብጦ አይጠጣም (ፓርቲው ሥልጣን ከያዘ በቀጣዩ ወር ሃያ ሁለተኛ አመቱን መድፈኑን ልብ ይሏል)፣ ዲሞክራሲ ህልውናችን ነው፣ ቀይ ምንጣፍ አናነጥፍም…›› ጅኒ ቁልቋል በሚሉ የእብሪት ገለፃዎች ማለፉ ነው፡፡ ከዚህም በላይ ሪፖርቱ በሀሰተኛና በማደናገሪያ ዘገባዎች የታጀለ እንደነበረ መታዘብ ተችሏል፡፡ ለማሳያነትም ያህል ጥቂቶቹን በአዲስ መስመር እጠቅሳለሁ፡- ‹‹ዕድገት›› ሲባል… የኢኮኖሚ ዕድገትን በተመለከተ ጠቅላይ ሚንስትሩ በሪፖርቱ ላይ ‹‹የሀገራችን ኢኮኖሚ ዕድገት ሂደት ሲታይ ላለፉት አስር ዓመት (ከ1996-2005) በየዓመቱ በአማካይ 10.9 በመቶ በማደግ ከፍ ባለ የእድገት ጉዞ (Trajectory) ውስጥ መሆኑን አመላክቷል›› ሲል ነግሮናል፡፡ ይሁንና አስሩን ዓመት ትተን የዘንድሮውን በመሬት ላይ ያለውን እውነት እንኳ ብንመለከት የሚያሳየው ተቃራኒውን ስለመሆኑ ለራሱም ቢሆን ይጠፋዋል ተብሎ አይታሰብም፡፡ በአገሪቱ ሥራ-አጥነት (በከተሞች 40 በመቶ መድረሱን ጥናቶች ይጠቁማሉ) በአስከፊ መልኩ ተንሰራፍቶ፣ ስደት ዕጣ-ፈንታ ተደርጎ ኩብለላ የዕለት ተግባር በሆነበት፣ ብዙሀኑ ኢትዮጵያዊ በኑሮ ውድነት እንደ ከባድ ማዕበል ወደላይ ጎኖ፣ ቁልቁል በአናት እየተተከለ በሚንገላታበት፣ ጎዳናዎች ቀን ቀን ልመና በወጡ ምንዱባን፣ ማታ ማታ ደግሞ ነፍሳቸውን ለማቆየት የሚውተረተሩ በዕድሜም በአካልም ትናንሽ የሆኑ ሴተኛ አዳሪዎች ተጥለቅልቆ… ባለበት በዚህ ዘመን ‹በየዓመቱ በአማካኝ 10 በመቶ እያደግን ነው› የሚልን አላጋጭ ሪፖርትን ሰምቶ በቸልታ ማለፉ ሰው የመሆን ጉዳይንም ፈተና ላይ መጣሉ አይቀርም፡፡ በዚህ ለሶስት ወራት በዘገየው ሪፖርት የዋጋ ንረትን ከአንድ አሃዝ እንዳያልፍ እየተሰራ ስለመሆኑም ተገልጿል፡፡ ከ1987 ዓ.ም ጀምሮ ከየምርጫው አንድ ዓመት በፊት በመለስ ዜናዊ ይቀርቡ የነበሩ ሪፖርቶች እንዲህ አይነት የዋጋ ንረት እንደሚቀንስ የ‹‹ሚያበስሩ›› እንደነበር ይታወሳል፡፡ የኃይለማርያምም ሪፖርት፣ ፓርቲው በምርጫ ዘመቻው ወቅት ሁሌ እንደ ስልት የሚጠቀምበትን ይህንን ጉዳይ አስጩኾ ከተለመደው የግብይት ሥርዓት አፈንግጦ መጠነኛ የዋጋ ማረጋጊያ በማድረግ የእሳት ማጥፊያ ሥራ ለመስራት ከመዘጋጀት ያለፈ ትርጉም ያለው ነገር የሚያመጣ ሆኖ አይደለም፡፡ አብዮታዊ ግንባሩም ቢሆን የምርጫው ማዕበል የሚጠራርገውን ጠርጎ፣ የሚወረውረውን ወርውሮ ማለፉ ላይ እርግጠኛ እንደሆነው ሁሉ፣ ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ የዋጋ ንረቱ ተመልሶ የቱንም ያህል ወደላይ ቢስፈነጠር የተቆጡ ድምፆች አደባባዩን እንደማይሞሉት ጠንቅቆ ያውቀዋል። ሌላው የሪፖርቱ አስቂኝ ክፍል የግብርናውን ዘርፍ የተመለከተው ነው፡፡ ይኸውም ካለፈው ዓመት የዘንድሮው በእጅጉ ማደጉን ገልፆ እንደምክንያት ያቀረበው ‹‹ዋናው የዕድገት መሰረት በመሬት ማስፋት ሳይሆን በምርታማነት የመጣ መሆኑን የሚያሳይ ነው›› የሚል ነበር፡፡ ይሁንና እዚህ ጋ የሚነሳው ጥያቄ የዘርፉ ባለሙያ መሆንን የማይጠይቅ ቀላልና ግልፅ ነው፡- የግብርና ቴክኖሎጂ መሻሻል በሌለበት፣ የሰው ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ በመጣበት (አማካይ የመሬት መጠን ከአንድ ሄክታር ያነሰ ሆኖ)፣ ማዳበሪያ ለፓርቲ አባላት ብቻ በሚታደልበት፣ የዝናብ ወቅትን ብቻ ጠብቆ በሚዘራበት እና መሰል ችግሮች ባጨለሟት ኢትዮጵያችን ምርታማነት ከመቼውም ጊዜ በላይ አደገ መባሉ እንዴት ተቀባይነት ሊኖረው ይችላል? …መቼም በመለኮታዊ ኃይል ከሰማይ በወረደ መና ነው ሊሉን አይችሉም፡፡ ካሉ ግን ምን ማድረግ ይቻላል! ሰውየው ኃይለማርያም፣ ፓርቲውም ኢህአዴግ ነውና፡፡ እጅግ የሚያሳዝነው የእነርሱ ዕድገት፣ ምርታማነት… ቅብርጥሶ የሚለው ፕሮፓጋንዳ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች በምግብ እጦት መጠቃታቸውን ዓለም አቀፍ ተቋማት እየዘገቡ ባለበት ወቅት መሆኑ ነው፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞም የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንደ መስከረም አደይ አበባ በየሜዳው መፍካቱን አብስረውናል፡፡ ይሁንና ሀገሪቱ እንኳን ለግዙፍ ፋብሪካዎች የሚሆን የኃይል አቅርቦት ቀርቶ፣ አነስተኛ ፍጆታ ያለውን የከተማ ነዋሪ የመብራት ፍላጎትም ማሟላት ያለመቻሏ ጉዳይ ፀሀይ የሞቀው፣ ዝናብ ያጨቀየው የአደባባይ እውነታ ነው፡፡ የግልገል ግቤ 3 ፕሮጀክትም ቢሆን፣ ኃይለማርያም ደሳለኝ እንደደሰኮረው በሚቀጥለው ዓመት ሥራ የሚጀመር አለመሆኑን ግንባታውን የሚያካሄደው ካምፓኒ አስቀድሞ ማሳወቁን ሰምተን አረጋግጠናል፡፡ ሌላው በሪፖርቱ ከተጠቀሱ ጉዳዮች ውስጥ ግርምት የሚያጭረው ከወራት በፊት በሳውዲ አረቢያ አሰቃቂ ጭካኔ የተፈፀመባቸውን ወንድም-እህቶችን በተመለከተ በአምስት መስመር ብቻ ተቀንብቦ የቀረበው ዘገባ ነው፡፡ የዚህን ሥርዓት ከኢትዮጵያዊነት መንፈስ ከመራቅም በላይ፣ መበስበሱን የሚያስረግጠው እንዲያ በ21ኛ ክ/ዘመን ሊፈፀም ቀርቶ ይታሰባል ተብሎ በማይታመን ጭካኔ ደማቸው ደመ-ከልብ ሆኖ ስለቀረውና አስክሬናቸው በጎዳና ላይ ስለተጎተተው ወገኖቻችን፡- ‹‹የሳዑዲ መንግስት በተለያየ ምክንያት ሕጋዊ የመኖሪያና የሥራ ፈቃዳቸውን ማስተካከል ያልቻሉ ኢትዮጵያውያን አገር ለቀው እንዲወጡ በወሰነው መሰረት…›› በማለት በሪፖርት ተብየው አቃሎ ማቅረቡ ነው፡፡ ይህ ጉዳይ ሁለት ነገር ያመላክታል፡፡ የመጀመሪያው ሥርዓቱ ለዜጎቹ ደህንነት ደንታቢስ በመሆኑ ቢያንስ በወረቀት ላይ እንኳን ነውረኛውን የሳውዲ መንግስት ለማውገዝ እና ወደፊትም ከእንዲህ አይነቱ ዲያብሎሳዊ ተግባሩ እንዲታቀብ ለማስጠንቀቅ አለመድፈሩን ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ በዚህን መልኩ ከተባረሩ ስደተኞች መካከል አሁንም ወደዛው የሞት ቀጠና ተመልሰው መሄዳቸው፣ ጠ/ሚንስትሩ እንዲያ የተዘባነነበትን ‹‹ዕድገት›› ልብ-ወለድ ማድረጉን ነው፡፡ መልካም አስተዳደር ሲባል… የኃይለማርያም ደሳለኝ ሪፖርት በደምሳሳው እውነት ለመናገር የሞከረው መልካም አስተዳደር ያለመኖሩን በተመለከተ ብቻ ነው፡፡ ለማሳያነትም የሚከተለውን ልጥቀስ፡- ‹‹በአገራችን ከፌዴራል ተቋማት ጀምሮ በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች ደረጃው የተለያየ ቢሆንም፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንደሚታዩ ሕዝቡ በተለያዩ መድረኮችና አገልግሎት በሚያገኝባቸው ሥፍራዎች ቅሬታዎች እያነሳ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡›› ከዚህ በተጨማሪም መንግስታዊ ጉድለቱ ከኪራይ ሰብሳቢነት አንስቶ፤ በመሬት አስተዳደር፣ በታክስ አሰባሰብ እና የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት በማስፈፀም ሂደት፣ በአገልግሎት ተቋማት ውስጥ የሚታይ የአመለካከት ችግር፣ የሥራ ተነሳሽነት አለመኖር፣ ግልፅነት እና ተጠያቂነት መጥፋትንም እንደሚጨምር ሪፖርቱ አትቷል፡፡ ይሁንና ሰዎቹ እንዲህ በድፍረት ያነበሩት ሥርዓትን ክሽፈት ቢያውጁም፣ ቅንጣት ታህል ‹የሕዝብ ተቃውሞ ሊነሳ ይችላል› የሚል ስጋት የለባቸውም፡፡ ስለምን? ቢሉ፣ በአንድ በኩል ስለዲሞክራሲ ማበብና የሕግ የበላይነት እየዘመሩ፤ በሌላ በኩል በእነዚህ ሁሉ ችግሮች ተተብትበው ሥልጣንን በገዛ ፍቃድ ካለመልቀቅም አልፎ ቀጣዩን ምርጫ አጭበርብሮ እና ተቀናቃኞችን ጨፍልቆ ለማሸነፍ ዝግጁ መሆን የሚቻለው በእኛይቱ መከረኛ ኢትዮጵያ ብቻ እንደሆነ ገና ድሮ ገብቷቸዋልና፡፡ ሌላው የአገሪቱን ሀብት በጠራራ ፀሀይ የመዝረፍ እውነታውን ለመረዳት ጠቅላይ ሚንስትሩ ሪፖርቱን ካቀረበበት ሁለት ቀን ቀደም ብሎ (በ14/8/06 ዓ.ም) የፌዴራል ዋና ኦዲተር የ2005ቱን የበጀት ዓመት በተመለከተ ያቀረበውን ሪፖርት ማየቱ ብቻ በቂ ነው፡፡ መስሪያ ቤቱ በተለያየ ምክንያት ከመንግስት ተቋማት በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ እንደባከነ የገለፀው የገንዘብ መጠን በድምሩ 3,207,752,247.05 (ሶስት ቢሊዮን ሁለት መቶ ሰባት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሀምሳ ሁለት ሺ ሁለት መቶ አርባ ሰባት ብር ከዜሮ አምስት ሳንቲም) መሆኑን በግላጭ አስቀምጧል፡፡ ይህ እንግዲህ በቀጥታ ከጥሬ ገንዘብ ጋር የተያያዘ ውድመት ነው፡፡ ከዚህ ሌላ በርካታ ችግሮችና ዘረፋዎች መኖራቸውን ሪፖርቱ በስፋት ዘርዝሯል፡፡ ለምሳሌ የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያን የተመለከተውን ማየት ይቻላል፡፡ ይህ መሳሪያ ሥራ ላይ መዋል ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስከ 2005 በጀት ዓመት መጨረሻ ድረስ ለግብር ከፋዩ ከተሸጠው ውስጥ 89 በመቶው አገልግሎት ላይ ቢውልም፣ የሽያጭ መረጃን ወደ መረጃ ቋት የሚያስተላልፈው 12 በመቶ ብቻ ሲሆን፤ የተቀረው 88 በመቶ ምንም ነገር እንደማያስተላልፍ ተገልጿል፡፡ እናሳ! ይህ ስለምን ሆነ? ለግብር ሰብሳቢ መስሪያ ቤቱ መረጃ የማያስተላልፉት የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያዎችስ በእነማን ድርጅቶች እጅ ውስጥ የሚገኙት ይሆኑ? …እውን! ጠቅላይ ሚንስትሩ ለዚህ መልስ ይኖረዋልን? የስኳር ኮርፕሬሽኖችን በተመለከተ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በሪፖርቱ ላይ ‹‹(አዳዲሶቹ) አብዛኛው የስኳር ፋብሪካዎቻችን በቀጣይ ዓመት ወደ ማምረት ተግባር ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል›› በማለት ቢገልፅም፤ የኦዲት ሪፖርቱ ግን ተቃራኒውን ነው የሚያረዳን፡፡ ይገነባሉ የተባሉት ፋብሪካዎች በኮርፕሬሽኑ የአምስት ዓመት ዕቅድ መሰረት ሁለመናቸው ተጠናቅቆ ወደ ማምረት እንደሚገቡ መገለፁ አይካድም፡፡ ነገር ግን የጣና በለስ ቁጥር አንድ እና ቁጥር ሁለት ግንባታ እስከ ጥቅምት 2005 ዓ.ም ያልቃል ቢባልም፤ በዛው ዓመት መጨረሻም ቁጥር አንድ 45 በመቶ፣ ቁጥር ሁለት 39 በመቶ ብቻ ሲጠናቀቅ፤ በኦሞ-ኩራዝ ደግሞ የፋብሪካው ግንባታ መጠናቀቅ በነበረበት ዓመት 42 በመቶ ብቻ የተሰራ መሆኑን ሪፖርቱ አጋልጧል፡፡ እንዲሁም እስከ ጥቅምት 2006 ዓ.ም ይጠናቀቃል የተባለው የወልቃይቱ ፋብሪካ የኦዲት ሪፖርቱ እስከተዘጋጀበት ጊዜ ድረስ ምንም አይነት የግንባታ ሥራው እንዳልተጀመረ ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም የተንዳሆ ስኳር ልማት ፋብሪካ በታቀደለት ጊዜ ባለመጠናቀቁ ምክንያት 5146.09 ሄክታር መሬት ላይ የነበረው የሸንኮራ አገዳ ምርት ዕድሜው በመራዘሙ ተበላሽቶ እንዲወገድ በመደረጉ፣ ፋብሪካው ማግኘት የሚገባውን 102,440,145.00 (አንድ መቶ ሁለት ሚሊዮን አራት መቶ አርባ ሺህ አንድ መቶ አርባ አምስት) ብር ተገቢ ባልሆነ መንገድ ያሳጣው እንደሆነ የኦዲት ሪፖርቱ አትቷል፡፡ ታዲያ ጠቅላይ ሚንስትራችን ‹በሚቀጥለው ዓመት ሥራ ይጀምራሉ› የሚለን የትኞቹን የስኳር ፋብሪካዎች ይሆን? እግዜር ያሳያችሁ! እንዲህ አይነት ያፈጠጠ ነጭ ውሸት የሚነግረን፣ ፕሮጀክቶቹን እስከዚህ ዓመት መስከረም ወር መጀመሪያ ድረስ በበላይነት ይመራ የነበረው አባይ ፀሀዬን አማካሪው አድርጎ ነው፡፡ የሆነው ሆኖ ይህ ሁኔታ የሚያመላክተው ሌላ ጉዳይ ቢኖር አቶ ኃይለማርያም ዛሬም ‹‹እመራዋለሁ›› ለሚለው አብዮታዊ ድርጅቱ ሩቅ የመሆኑን ምስጢር ነው፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትርነት በተሾመ ማግስት፣ አቶ መለስ ማሌሊትን ቀብሮ ስለልማታዊ መንግስት ከማንችስተር እስከ ኮሎምቢያ ዩንቨርስቲዎችና ዓለም አቀፍ የአደባባይ መድረኮች መከራከሩን ያልሰማ የሚመስለው ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በመጀመሪያው ከውጭ ጋዜጠኛ (ከቪኦኤው ፒተር ላይን) ጋር ባደረገው ቃለ-መጠየቅ ላይ ‹‹እኛ ተራማጅ ግራ-ዘመም ነን›› ሲል የተደመጠበትም መግፍኤ ይኸው ይመስለኛል፡፡ ኤርትራ ሆይ! ብረሳሽ… ጠቅላይ ሚንስትሩ ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት፣ አቶ ግርማ ሰይፉ መንግስት የኤርትራንና የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማቀራረብ የሚያደርገውን ጥረት አስመልክቶ ያለውን አቋም በተመለከተ ላነሳው ጥያቄ፣ የሰውየው ምላሽ ከእውነታው ፍፁም ያፈነገጠ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ የኃይለማርያም ማብራሪያ ሁለቱ ሕዝቦች የቀድሞ ግንኙነታቸውን መልሰው እንዲያጠናክሩ ‹‹ኢትዮጵያውያን የኃይማኖት አባቶች እና ምሁራኖች ለሚያደርጉት ጥረት መንግስት ድጋፍ እያደረገ ነው›› የሚል ሲሆን፤ ኤርትራን በተመለከተ ደግሞ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ በአሸባሪነት ፈርጆ ማዕቀብ ጥሎ እያሰቃያት ከመሆኑም በላይ በአካባቢው ከኢትዮጵያ በስተቀር ተሰሚነት ያለው ሀገር ያለመኖሩን የሚያመላክት አንድምታ አለው፡፡ ይህ ግን ምን ያህል እውነት ነው? ብለን ስንጠይቅ፤ በኤርትራ መገንጠልም ሆነ በለንደኑ ኮንፈረንስ የህወሓትን የበላይነት ያስረገጡትና በአሜሪካን አስተዳደር ተሰሚነት ያላቸው አምባሳደር ኸርማን ኮኽን ኤርትራን ከ‹‹ብርዱ›› ለማውጣት አሜሪካም ሆነች የተባበሩት መንግስታት የጣሉትን ማዕቀብ እንዲያነሱ እና ድንበሩ እንዲሰመር በአደባባይ መጮኽ ከጀመሩ መሰንበታቸውን እንረዳለን፡፡ እንዲሁም ሌላኛው አምባሳደር ዴቪድ ሺንም ኢትዮጵያ ባድመን እስከመስጠት ከሄደች በሁለቱ ሀገራት ሰላም ማምጣት እንደሚቻል ደጋግመው ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ እናም እነዚህን ሰዎች ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ አሜሪካውያን ፖለቲከኞች ኤርትራ እ.ኤ.አ. ከ2009 ዓ.ም ወዲህ ሽብርተኝነትን ከመደገፍ መቆጠቧን ጠቅሰው በመከራከር ላይ መገኘታቸው እውነታውን ፍንትው አድርጎ ሳያል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ‹‹ኢትዮጵያውያን የኃይማኖት አባቶችና ምሁራኖች…›› ንግግርም በሬ ወለደ ይመስለኛል፡፡ ከዚህ ባለፈ የሀገሬ መንግስት ለተከታታይ አስራ ስድስት አመታት ‹ኤርትራ ሆይ! ብረሳሽ ቀኜ ይርሳኝ›ን የሚዘምረው ሀገር-በቀል ተቀናቃኞቹን በስመ-ሻዕቢያ መጨፍለቅ ሲፈልግ ብቻ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ እኛ ቀጥለናል! ግንባሩ ‹‹ባለራዕይ›› በማለት ካቆለጳጰሰው የቀድሞ ሊቀ-መንበሩ አቶ መለስ ህልፈት በኋላ፣ በጠባብ ብሔርተኞችና ጥቅመኞች በመሞላቱ መተካካቱን ተከትሎ ይፈረካከሳል የሚል ከውስጥም ከውጪም የሚሰማ ሹክሹክታ ነበር፡፡ በርግጥም የኃይለማርያም ወደ መንበሩ መምጣት ‹‹በአማራና ኦርቶዶክስ የምትመሰለው ሀገር፣ የአናሳውም ሆናለች›› ከሚለው የአቦይ ስብሐት እንቶ ፈንቶ ውጪ፣ ከተጠበቁት ሁነቶች ብዙዎቹን (በተለይ ሥርዓታዊ ልልነት ይፈጠራል የሚለው) በገቢር ከመስተዋል አልታደጋቸውም፡፡ ለዚህም ሁለት ማሳያዎችን እጠቅሳለሁ፡፡ የመጀመሪያው ባሳለፍነው ሳምንት በጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀረበው ሪፖርትና ማብራሪያ ላይ ተደጋግሞ የተነሳው ‹‹የአፈፃፀም ችግር›› የሚለው ነው፡፡ የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ተብሎ ከበሮ ከተደሰቀለት የተቀመጠ ግብ አኳያ፣ ነባራዊው ሁኔታ ስምም አለመሆኑን ራሱ ኃይለማርያምም ‹‹የአፈፃፀም ጉድለት›› በሚል የዳቦ ስም ሊያሳብብ ከመሞከር በቀር አልካደውም፡፡ አንድ ማዕከላዊ መንግስትን የሚመራ ግንባር፣ ሊያውም እስከ ቤተሰብ የወረደ የኃይል ማዕከል ለመገንባት የሚጥር ስብስብ፤ ከተሞችን እያሰቃየ ላለው የመሰረታዊ ግልጋሎቶች ዕጦትና የተቀመጡ ዕቅዶች አለመሳካት ይህን በመከራከሪያነት ማቅረቡ፤ የስርዓቱ ተቋማት መፈረካከስን ከማስረገጥ ያለፈ የሚነግረን ምስጢር የለውም፡፡ ሌላኛው የአማካሪዎቹ ስብስብ ጉዳይ ነው፡፡ ሰውዬው ከጎኑ የሰበሰባቸውን ጉምቱ ፖለቲከኞች ትተን፤ ለእያንዳንዱ ጉዳይ ካውንስል የማቋቋም ፍጥነቱን ብናስተውል ስርዓቱ በመለስ ዘመን የነበረውን ጥብቅነት አጥቶ መዋለሉን እንረዳለን፡፡ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ እንዲመራ ካስቀመጠው ዶ/ር ደብረፅዮን ውጪ፣ ‹‹የኢኮኖሚ ካውንስል›› በሚል አይረቤ ስም ለማቋቋም መሞከሩ ሳይበቃ፤ በባጀት ዕጥረት እየተሰቃየ ያለውን አስተዳደሩን ለመታደግ የፋይናንሻል ምንጮችን ከውጪ የሚያፈላልግ ሌላ ካውንስል መሰል ስብስብ ማደራጀቱን ስንታዘብ፤ ስርዓቱ ቢያንስ እንደ መለስ ዘመን መቀጠል በማያስችል ወላዋይነት /Brittle state/ ለመፈተኑ ጥቁምት ይሰጠናል ብዬ አስባለሁ፡፡ በተለይም ጠቅላይ ሚንስትሩ በሪፖርቱ ላይ የአገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ፍላጎት ለማሟላት መንግስት የሐዋላ አግልግሎትን ማጠናከር እንዳለበት ከመግለፅ ባለፈ፣ ከ2000 ዓ.ም መጀመሪያ አንስቶ የህንዱን ካራቱሪ እና ሳውዲ ስታርን ጨምሮ ለበርካታ ባለሀብቶች ስለተሰጠው ሰፋፊ የእርሻ መሬት አንዳችም ነገር ትንፍሽ አለማለቱ የክስረቱ ዋነኛ ማሳያ ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም በወቅቱ ከመሬት ቅርምት ጋር አያይዘው የተቃውሞ ድምፃቸውን ላሰሙ ምሁራንም ሆነ ‹‹አንድ ሄክታር መሬት በሃያ ብር›› መሰጠቱን በመኮነን የድርጊቱን ኢ-ፍትሓዊነት በዘገባው ለገለፀው ታዋቂው ‹‹ኒዎርክ ታይምስ›› ጋዜጣ፣ መለስና ጓዶቹ መከራከሪያ አድርገው ያቀረቡት ‹‹በአጭር ጊዜ ውስጥ የውጭ ምንዛሬ ችግራችንን ይቀርፋል፣ የቴክኖሎጂና የሙያ ሽግግር እንዲደረግ ያስችላል›› የሚል እንደነበረ አይዘነጋም፡፡ ግና፣ ዛሬ ይህ ጉዳይ ሕልም ሆኖ ለውጭ ምንዛሪ ሐዋላን የሙጥኝ መባሉን እየሰማን ነው፡፡ እንዲሁም በራሱ በመለስ ዜናዊ በ2005 ዓ.ም በርግጠኝነት መውጣት እንደሚጀመር የተነገረለት የነዳጅ ክምችትም ቢሆን፣ ‹‹ውሾን ያነሳ…›› እንዲሉ የተዘጋ ፋይል ሆኗል (በነገራችን ላይ በፓርላማው. የፓርቲው ካድሬዎች ባለስልጣናቱ ላይ የሚያዘንቡት የጥያቄ እሩምታ የሚያመለክተው፣ ፓርላሜንታዊ ዴሞክራሲ ዘግይቶ ወደ ኢህአዴግ ሰፈር መምጣቱን ሳይሆን፣ የፓርቲውን የውስጥ የዕዝ ተዋረድ መሰነጣጠቁን እና ቡድንተኛነት ግንባሩን እያመሰው መሆኑን ነው፡፡ በተቀረ ከዚህ ውጪ ያለው መከራከሪያ ሁሉ ጥሩ የአደባባይ ቧልት ከመሆን የሚያልፍ አይመስለኝም) የሆነው ሆኖ ከላይ ኃይለማርያምን ያብራሩልናል ብዬ ለመጥቀስ ከሞከርኳቸው ጭብጦች በእጅጉ ባለፈ፣ ሪፖርቱን ያቀረበበት ተአብዮ እና የማንአለብኝነት መንፈስ በቅድመ-ምርጫው አንድ ዓመት ውስጥ አንዳችም የፖለቲካ ማሻሻያ እንዳትጠብቁ የሚለው ዋነኛው ሲሆን፤ አቦ ሌንጮ ለታ ‹‹ሰዎች አሳስተውታል›› እንዳለው፤ ዙሪያው ያሉት አለቆች እንዳዘዙት፤ ‹እኛ እየረገጥናችሁ እንቀጥላለን፣ እናንተም በተጨቋኝነታችሁ አዝግሙ› የሚለው ደግሞ ሌላኛው ውስጠ-ወይራ ጥብቅ መልእክቱ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ በመጨረሻም ጠቅላይ ሚንስትር ኃ/ማርያም ጥር 2003 ዓ.ም. ‹‹ምዕራፍ›› ከተሰኘ ኃይማኖታዊ መጽሔት ጋር ቃለ-መጠይቅ ባደረገበት ወቅት ‹‹ከመጽሐፍ ቅዱስ ደስ የሚልዎት ቃል የቱ ነው?›› በሚል ለቀረበለት ጥያቄ የሰጠውን ምላሽ፣ አንድም ዛሬ የሚከተለውን መንገድ ቆም ብሎ እንዲፈትሽ ለማስታወስ፤ ሁለትም ለዚህ ተጠይቅ መደምደሚያ ይሆን ዘንድ ወደጃለሁና እንደሚከተለው አሰፍረዋለሁ፡- ‹‹መጽሐፍ ቅዱስን እወደዋለሁ፡፡ የዮሴፍ፣ የዳዊት፣ የሙሴ ሕይወት በጣም ይለውጡኛል፡፡ የእነዚህ ቅዱሳን ሕይወት በጣም ያንጹኛል፡፡ ዳንኤልም በጣም ጠቢብ ነው፡፡ ስለዚህም እንደርሱም መሆን መልካም እንደሆነ አስባለሁ፡፡›› ወንድም ኃይለማርያም ደሳለኝ፡- የልብህን መሻት አምላክ ይሙላልህ!!

Video: የእሪታ ቀን፡- ይህ ቪዲዮ ከአንድነት ሰልፍ የተቀነጨበ ሲሆን ሙሉውን ቪዲዮ ከሰዓታት በኋላ እንለቃለን

 መታሰቢያነቱ በግፍ ለተገደሉ የዮኒቨርቲ ተማሪወች።

$
0
0

ብርሀን አህመድ

       መንገድ ላይ ቀረሁ!!
የልቤን፣አውጥቸ__ ሳልናገር፣ለስው፣
አድካሚ፣ጉዞየን__ ሄጀ፣ሳልጨርሰው፣
እንዳሻኝ፣እንደልብ__ ሳልፅፍ፣ሳይነበብ፣
በቡቃያኔቴ__ አፍርቸ ሳላብብ።

ተምሪ፣ጨርሸ__ ሀገሬን፣ሳልጠቅም
አግብቸ፣ወልጀ__ ልጅ፣አቅፊ፣ሳልሰም፣

እናቴን፣ሳልጦራት__ አባቴን፣ሳልረዳ
አምሮብኝ፣፣ሳልታይ__ ወጥቸ፣ከጋዳ
አናቴ ላይ ጥይት __ ጉኔን፣ሰለት ወግቶተኝ
በወጣትነቴ መንገድ ላይ ቀ  ረ ሁ  መሪ።

pen

ዛሬ በኦሮሚያ ክልል በደምቢዶሎ ከተማ ሕዝብ ላነሳው ጥያቄ የመንግስት ምላሽ ጥይት ሆነ፤ ውጥረቱ ቀጥሏል

$
0
0

የአንዲት ሴት ልጅ ሕይወት እንደጠፋ ተነግሯል

Breking News(ዘ-ሐበሻ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን አዲሱን ማስተር ፕላን በመቃወም በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ትምህርት ተቋሞች ውስጥ የተነሳው ተቃውሞ እየተቀጣጠለ በተለያዩ ከተሞች እየተዛመተ ሲሆን በዛሬው ዕለት በደምቢዶሎ ከተማ በተደረገ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የመንግስት ወታደሮች የሃይል እርምጃ መውሰዳቸውን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ከስፍራው ዘገቡ።

እንደምንጮቻችን ዘገባ ከሆነ ደምቢዶሎ ከተማ የመንግስት ወታደሮች በሰልፈኞች ላይ የጥይት እሩምታ ያወረዱ ሲሆን ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ወገኖች መጎዳታቸውንና የህክምና መስጫ ጣቢያዎችም በቁስለኞች መጨናነቃቸውን ዘጋቢዎቻችን ገልጸዋል። በዛሬው ተቃውሞ ምን ያህል ሰዎች እንደሞቱ ምንጮቻችን ያደረሱን መረጃ ባይኖርም ከሌሎች ወገኖች ባገኘነው መረጃ የአንዲት ለጊዜው ስሟና ማንነቷ ያልታወቀ ሴት ልጅ ሕይወት ጠፍቷል።

ከአዲስ አበባ 650 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ደምቢዶሎ ከተማ ያለው ውጥረት ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ አልበረደም።

ዘ-ሐበሻ ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሷት ትመለሳለች።

ይህ በእንዲህ እንዳለ መንግስት “አዲስ አበባን እና የኦሮሚያ ልዩ ዞንን በልማት ለማስተሳሰር የተዘጋጀው የጋራ ማስተር ፕላን ልዩ ዞኑን ብሎም አጠቃላይ የኦሮሚያን ክልል የበለጠ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው” ሲል ገለጸ። መንግስት በምእራብ ሸዋ ዞን የዞኑ ነዋሪዎችና የመንግስት ተወካዮች ጋር አካሄድኩት ባለው ውይይት “በውይይቱ በዞኑ የተወሰኑ አካባቢዎች ተከስቶ የነበረውን ሁከትና ብጥብጥ ተከትሎ በጠፋው የሰው ህይወትና የንብረት ውድመትን አውግዘዋል” ሲል በሚቆጣጠራቸው ሚድያዎች በኩል ዜናውን አሰምቷል። ይህን ውይይት የመሩት ውይይቱን የመሩት አፈጉባኤ አቶ አባዱላ ገመዳና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስተር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ሪፎርም ክላስተር አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር ወይዘሮ አስቴር ማሞ “ማስተር ፕላኑ የኦሮሚያን ልዩ ዞንና የክልሉን ተጠቃሚነት የበለጠ የሚያረጋግጥ ነው” ሲሉ መናገራቸውን የመንግስት ሚድያዎች ዘግበዋል።

(የሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ) ከወገብ በላይ ታቦት ከወገብ በታች ጣኦት!!

$
0
0

ከኢትዮ ተዋሕዶ

ህሊናዬ ያለእረፍት ይናጣል በሃሳብ ቅብልብሎሽ አድማስ ይሻገራል፡፡መቸም ህሊናችን አንድ ግዜ ክፉውን ሌላ ጊዜ በጎውን ማውጠንጠኑ የተለመደ ገቢር ቢሆንም ህሊናዬን በቁጣና በቁጭት ያደነቆረኝን ነገር በልቤ አብሰልስዬ በአንደበቴ መስክሬ የእርካታ ጣሪያ ላይ መድረስ አልተሳነኝምና ቁጭት ያቀረረ ብእሬን አንስቼ በጦማር ልፋለመው ገባሁ፡፡በቅድሚያ ክቡር ንዑድ የሆነ ሰለምታዬ ይድረሳችሁ፡፡
debereselam Minnesota
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ለዘመናት በሊቃውንት አባቶች ከታላቁ መፃህፍ ከመፅሐፍ ቅዱስ በተጨማሪ ህገ መንፈሳዊ በሆኑት ፍትሃ ነገስት(The Law of the Kings)፣ቃለዓዋዲ፣ ሐይማኖተ አበው እና ሌሎችም አዋልደ መፃህፍት በመታገዝ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ የዋጃትን ቅዱሳን አባቶች ስለ እውነት ብለው እንደ ስንዴ ተቆልተው እንደ አክርማ ተሰንጥቀው በዱር በገደል እንዲሁም በበረሀ ተቅበዝብዘው ቅጠል በልተው አፈር ልሰው ድንጋይ ተንተርሰው የቤተክርስቲያንን ህልውና ከፀና ሰርዓቷ ጠብቀው አኖረዋል፡፡

የጉድ ሃገር ገንፎ እያርደ ይፋጃል” እንዲሉ አለማዊ ክብርና ዝናን ለመላበስ በመሻት ከሙሽራው ክርስቶስ ውዳሴ በላይ የኔ ስምና ክብር ይቅደም በማለት በበዓለ ሆሳዕና ቅዳሴ የተስተጓገለበትን የሚኖሶታው ደብረ ሰላም መድሐኒያለም በአርምሞ ማለፍ ከህሊና ጋር መቃቃር እንዲሁም የልቦና መባከን ስለሆነብኝ ትንሽ የግሌን የአስተሳሰብ ልኬት እና ግንዛቤ ከመንፈሳዊ ህግ ጋር በማዋሃድ ላወጋችሁ ወደድኩ ፡፡ሆሳዕና በልዩ ሁኔታ የሚከበር ጌታችንን ክርስቶስ በእየሩሳሌም ከሚጠቡ ህፃናት አንደበት አንስቶ እሰከ ቤተፋጌ ድንጋዩች ድረስ “ሆሳዕና በዓርያም በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ አርሱ ብሩክ ነው″ ብለው ያመሰገኑበት ተዓምራታዊ እለት እና አንደኛው አበይት በዓል ነው፡፡ እናም በዚህ እለት ኢትዮጳያ ካለው ቅዱስ ሲዲኖዶስ ለኒዮርክና አካባቢዋ የተላኩት አቡነ ዘካሪያስ በስርዓተ ቅዳሴው የእኔን ስም በመግለፅ ሊቀደስ ይገባል ካለሆነ ቅዳሴው ተስተጓግሎ ቤተክርስቲያኒቷ እንድትዘጋ የሚል ትዕዛዝ አስተላለፉ፡፡ለሃያ አመታት በዚህ ስርዓት ሲተዳደሩ የነበሩ ህገ እግዚአብሄርን የሚያከብሩ ካህናትና ዲያቆናት ከህዝበ ክርስቲያኑ ጋር ጌታን ሲያመሰግኑ ዋሉ፡፡ የነገስታቱ ምድራዊ ጥንካሬና ጉልበት ያስፈራቸው ካህናት ቅዳሴውን ትተው ምድራዊውን ንጉስ ሊያመስግኑ ከሆሳዕና ተለዩ ከፈሪሳዊያንም ጋር አበሩ፡፡ከሙሽራው በላይ መድመቅና መክበር የፈለጉ ሚዜዎች መሆን ፈልገው እንጂ ከማያልፈው የክርስቶስ ክብር የእነሱን ዘለቄታ የለሽ ዝና ማስቀደም አልነበረባቸውም(የመንግስት ቀኝ ክንፍ ካለሆኑ በቀር) ደግሞም ቤተክርስቲያን ስለአለም ሁሉ የምትማልድ እንጂ ለህዝብና አህዛብ፣ ለቤተክርስቲያን ኃላፊዎችና ለቤተመንግስት ባለስልጣን አልያም ላለው ለሌለው ብላ እግዚኦታ የምታስብል አይደለችም፡፡ ለቤተክርስቲያን አገልጋይም በተለየ መልኩ በማዕረግ ፀሎት መደረግ አለበት ከተባለ በስርዓተ ቅዳሴው “ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት፣ጳጳሳት፣ ኤጲስ ቆጶሳት፣ ቀሳቀወስት ወዲያቆናት” በሚል ሀረግ ይማልዳል፡፡

ስለውግዘት መፅሐፍ ቅዱስ (መፅሐፈ ሔኖክ ምዕራፍ 36 ቁጥር 15) እንዲህ ይላል፡- "የማይገባ ግዝትን ለምትፈፅሙ ለናንተ ወዮላችሁ ስለ ኃጢያታችሁ ድህነት ከናንተ ይራቀ እንደስራችሁ መጠን ፍዳውን ትቀበላላችሁና ለባልንጀራችሁ ክፉ ምላሽ ልምትመሱ ለናንተ ወዮላችሁ"፡፡ በፍትሃ ነገስትም ላይ እንዲህ የሚል ኃያል ቃል እናገኛለን "አለቃው ህዝቡን የሚመክራቸው በውግዘት ያይደል በመስቀል የሚያስራቸው ይሁን በማይገባ አያውግዝ፡፡ሰዎችን ሊያሳዝናቸውና ፈርተው እንዲገዙለት ፈልጎ በማይገባቢያወግዝ እርሱ ከእግዚአብሐየር ዘንድ የታሰረ የተወገዘ ይሁን፡፡ ካህናትም በእውነት ይቋቋሙት ይላል፡፡ በተፃራሪ ለግል ክብርና ዝና ውግዘት ማድረግ ተገቢ አይደለም ተደጋጋሚ ምክር ሳይደረግ ሊቃውንተ ቤተክረስቲያን ጉባዔ ሳይቀመጡ ውጉዝ ከመዓርዮስ ማለት ወፈ ገዝት እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ይናገራሉ፡፡ሰለስቱ ምዕት(318ቱ ሊቃውንተ ቤተክርሰቲያን) አርዮስን በተደጋጋሚ መክረውና ዘክረው በነቂያ ጉባዔ እንዳወገዙት ልብ ይሏል ይህም የሆነው ለግል ክብርና ዝና ሳይሆን ከባድ ሐይማኖታዊ ክህደት በመፈፀሙ ነው፡፡

ስለውግዘት መፅሐፍ ቅዱስ (መፅሐፈ ሔኖክ ምዕራፍ 36 ቁጥር 15) እንዲህ ይላል፡- “የማይገባ ግዝትን ለምትፈፅሙ ለናንተ ወዮላችሁ ስለ ኃጢያታችሁ ድህነት ከናንተ ይራቀ እንደስራችሁ መጠን ፍዳውን ትቀበላላችሁና ለባልንጀራችሁ ክፉ ምላሽ ልምትመሱ ለናንተ ወዮላችሁ”፡፡ በፍትሃ ነገስትም ላይ እንዲህ የሚል ኃያል ቃል እናገኛለን “አለቃው ህዝቡን የሚመክራቸው በውግዘት ያይደል በመስቀል የሚያስራቸው ይሁን በማይገባ አያውግዝ፡፡ሰዎችን ሊያሳዝናቸውና ፈርተው እንዲገዙለት ፈልጎ በማይገባቢያወግዝ እርሱ ከእግዚአብሐየር ዘንድ የታሰረ የተወገዘ ይሁን፡፡ ካህናትም በእውነት ይቋቋሙት ይላል፡፡ በተፃራሪ ለግል ክብርና ዝና ውግዘት ማድረግ ተገቢ አይደለም ተደጋጋሚ ምክር ሳይደረግ ሊቃውንተ ቤተክረስቲያን ጉባዔ ሳይቀመጡ ውጉዝ ከመዓርዮስ ማለት ወፈ ገዝት እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ይናገራሉ፡፡ሰለስቱ ምዕት(318ቱ ሊቃውንተ ቤተክርሰቲያን) አርዮስን በተደጋጋሚ መክረውና ዘክረው በነቂያ ጉባዔ እንዳወገዙት ልብ ይሏል ይህም የሆነው ለግል ክብርና ዝና ሳይሆን ከባድ ሐይማኖታዊ ክህደት በመፈፀሙ ነው፡፡

ደግሞም እኮ በድርጊት እንጂ በስም ሰማዕትነትን የተቀበለ የሰው ዘር የለም (መብራቱን እስከ ዘይቱ የያዘም አይደል ከሙሽራው ጋር ሰርጉን የሚታደም?)፡፡

ከታሪክ የማይማር ታሪክን ይደግማል እንዲሉ ፈሪሳውያንና ሰዱቃዊያን በሆሳዕና እለት ህዝቡ የዘንባባ ዝንፃፊ እና የለበሱትን ልብስ በማንጠፍ ጌታ በውርንጭላይቱ ላይ ሆኖ እንዲያልፍ በማድረግ “ሆሳዕና በዓርያም በእግዚበሔር ስም የሚመጣ አርሱ ብሩክ ነው″ ብለው ሲያመስግኑ ለእነሱ አልተዋጠላቸውምና መምህር ሆይ ለምን ዝም በሉ አትላቸውም አሉት ምስጋና የባህሪ ገንዘቡ ነበርና እነሱ ዝም ቢሉ የቢታኒያ ድንጋዮች ያመሰግኑኛል አላቸው፡፡ እውነትም ድንቅ ነበር የቤተ ፋጌ አለቶች ድምፅ አውጥተው አመሰገኑት ዛሬም ይሄ ነው የተፈፀመው ፈሪሳውያንና ሰዱቃዊያን አናመሰገንም ሲሉ በበዓለ ሆሳእና በደብረ ሰላም መድሐኒያለም የቤተ ፋጌ አለቶች ድመፅ አውጥተው አመሰገኑት (ከቢታኒያ ድንጋይ ከማነስ ይሰውረን)፡፡ አቡነ ዘካሪያስም መፅሐፍ ቅዱስ በማይፈቅደው ከቤተክርስቲያን የህግ መፅሐፍ ከሆነው ከፍትሃ ነገስት ጋር በሚጣረስ መልኩ የግዝት ትዕዛዝ አስተላለፉ (እንደማስተባበያ ሥልጣነ ክህነታቸው ተያዘ እንጂ አልተወገዙም የሚል ጉንጭ አልፋ ምክንያት እንደ ምክኒያት ቢቀርብም &እዚች ጋር አንድ ቀልድ ቢጤ ትዝ አለችኝ ሰዎቹ በሰውዬው ሀብትና አውቀት እጅጉን ይቀኑና ህይወቱን እስከማጥፋ የሚደረስ ቅናት ያድርባቸዋል እናም በሚመላለስበት ቦታ አዘውትረው ይጠብቁት ነበርና አንደ ቀን አድፍጠው በሚጠብቁበት ሰዓት የሰውየው የበኩር ልጅ ያገኛቸዋል ወትሮውንም አባቱን ሊያጠፉት እንደሚፈልጉ ይሰማ ነበርና የያዙትን ስለት በማየት አባቴን ልትገሉት ነው አይደል ሲላቸው አንደኛው ፈጠን ብሎ አይደለም ባክህ የእናትህን ባል ነው አለው፡፡ግዝትና ክህነትን መያዝ ምን አለያየው ሁለቱም ግልጋሎትን የሚከለክሉ አይደሉም እንዴ ቂቂቂቂቂ)

ግዝት በቤተክርስቲያን ሃይማኖትን ለካዱ እና በነውር ለተገኙ ሰዎች በተለይም በካህናት ላይ የሚተላለፍ የመጨረሻው የፍርድ ውሳኔ ነው።ይህ አንድን ካህን(ሰው) ከማኅበረ ክርስቲያን የመለያ ውሳኔ የሚተላለፈው ደግሞ ተጨባጭ የሆኑ የኃይማኖት ክህደትና የምግባር ብልሹነት ሲቀርቡ ብቻ ነው።
ስለውግዘት መፅሐፍ ቅዱስ (መፅሐፈ ሔኖክ ምዕራፍ 36 ቁጥር 15) እንዲህ ይላል፡- “የማይገባ ግዝትን ለምትፈፅሙ ለናንተ ወዮላችሁ ስለ ኃጢያታችሁ ድህነት ከናንተ ይራቀ እንደስራችሁ መጠን ፍዳውን ትቀበላላችሁና ለባልንጀራችሁ ክፉ ምላሽ ልምትመሱ ለናንተ ወዮላችሁ”፡፡ በፍትሃ ነገስትም ላይ እንዲህ የሚል ኃያል ቃል እናገኛለን “አለቃው ህዝቡን የሚመክራቸው በውግዘት ያይደል በመስቀል የሚያስራቸው ይሁን በማይገባ አያውግዝ፡፡ሰዎችን ሊያሳዝናቸውና ፈርተው እንዲገዙለት ፈልጎ በማይገባቢያወግዝ እርሱ ከእግዚአብሐየር ዘንድ የታሰረ የተወገዘ ይሁን፡፡ ካህናትም በእውነት ይቋቋሙት ይላል፡፡ በተፃራሪ ለግል ክብርና ዝና ውግዘት ማድረግ ተገቢ አይደለም ተደጋጋሚ ምክር ሳይደረግ ሊቃውንተ ቤተክረስቲያን ጉባዔ ሳይቀመጡ ውጉዝ ከመዓርዮስ ማለት ወፈ ገዝት እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ይናገራሉ፡፡ሰለስቱ ምዕት(318ቱ ሊቃውንተ ቤተክርሰቲያን) አርዮስን በተደጋጋሚ መክረውና ዘክረው በነቂያ ጉባዔ እንዳወገዙት ልብ ይሏል ይህም የሆነው ለግል ክብርና ዝና ሳይሆን ከባድ ሐይማኖታዊ ክህደት በመፈፀሙ ነው፡፡

መቸም ዲያብሎስ በእድሜ እንጂ በተንኮል የማይበልጠን ተመፃዳቂ ለምድ ለባሽ ተኩላዎች ስለሆንን እንጂ ከእውቀትና ከመንፈሳዊ ብስለት ጋር የማይስማማ ቅዱሳን በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው ከፃፏቸው የህግ መፅሕፍት ጋር በሚጣረስ መልኩ ባልተባረከነ በአራቱም የቤተክርስቲያኑ አቅጣጫ በቅብዓ ሜሮን ባልተባረከበት ብዙ ተገቢ ስርዓተ ቤተክርስቲያን ባለተፈፀመበት አዲስ ቤተክርስቲያን ከሶስት ሳምንት በላይ ስርዓተ ቅዳሴ መፈፀም ምን ይባላል? ደግሞስ ለብዙ ዘመናት የጌታ ስጋና ደም ሲፈተትባት የነበረችን ቅድስት ቤተክርስቲያን ይሄንን በረት አሳማ አርቡበት ብሎ ናቡከደነፆራዊ ድፍረት የተሞላበት ስድብ መሳደብ መቸም ሚኒሊክ ቤተመንግሰት ካሉት ነገስታት የተላከ እንጂ ከሰማዩ አባት የተወረሰ መንፈሳዊ ብስለት አይደለም፡፡

ሌላው አስነዋሪ ክስተት አላዋቂ መካር የፍዳ ማከማቻ መሆኑ ያልተረዱት የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የበላይ አሰተዳዳሪ አባ ዘርዓ ዳዊት በትንሳኤ ሌሊት አለም ከአመተ ፍዳ ወደ አመተ ምህረት በተሸጋገረበት አዳም ከዲያብሎስ እስራት ወጥቶ በክርስቶስ እቅፍ በዋለበት በዚያች የድህነት ብስራት በሚበሰርበት የምህረት እምቢልታ በሚለፈፍበት የነፃነት ነጋሪት በሚጎሰምበት ትንሳኤ ክርስቶስ በሚዘመርበበት እለት የአስታራቂነት ሚና ከሚጠበቅበት መንፈሳዊ አባት ቤተክርሲቲያኗ ግልፅ ያልሆነ በጉባዔ ባለተወሰነ የካህናቱና ዲያቆናቱ ምግባር ፅድቅ ይሁን ኩነኔ ባልተለየበት ለማህበረ ምዕመኑ የካህናቱንና የዲያቆናቱን ውግዘትና የስልጣነ ክህነት እስር መለፈፍ ምን ይሉታል? (እስራት የባህሪ ገንዘቡ ከሆነው የኢትዮጵያ መንግሰት ካልተላኩ በቀር)፡፡ እናም ቅዱስ አባታችን የቀደመውን አስቡ እግዚአብሔር ለሁለት አምላክ መገዛት አትችሉም በማለት ቀናተኛ አምላክ መሆኑን በአውደ ምህረቱ ትሰብኩልን የለ እናንተም ወይ ምድራዊ ክብራችሁን አልያም በመስቀል ላይ የዋለውን አምልኩ አልያ ከወገብ በላይ ታቦት ከወገብ በታች ጣኦት ሆኖ በቤተክርስቲያን መክበር አይቻልም፡፡
ናቡከደነፆራዊ ድፍረታችሁን ትታችሁ የቀደመውን አስቡ!!!

እግዚአብሔር ለቤተክርስቲያናችን ህብረትን ፍቅርን አንድነትም ይስጥልን!!!

Sport: የጣልያን እግር ኳስ የተኛበት አልነቃም

$
0
0

kaka
በጣልያን የክለብ ባለቤቶች ለበርካታ ዓመታት የሚፈጠሩ ችግሮችን ሁሉ ከወለሉ በታች ሲሸሽጉ ከርመዋል፡፡ ኪሳራው በሚፈርሙ ውድ ተጨዋቾች እና ለይምሰል በሚታየው ሀብት ተጋርዷል፡፡ ባለፉት ጥቂት አስርት ዓመታት ሊጉ እየተጎዳ እና እየጠወለገ ሲሄድ በቀላሉ እንዳይታወቅ ያደረገውም ይኸው ሃቅ ነው፡፡ በ1990 ጀርመን በጣሊያን የተዘጋጀውን የዓለም ዋንጫ አሸነፈች፡፡ ከቡድኑ አባላት መካከል ደግሞ ዘጠኙ የሚጫወቱት በጣሊያን ነበር፡፡ በብዙሃኑ ይታወቁ ከነበሩት መካከል የርገን ክሊንስማን፣ ሎተር ማታየስ እና ቶማስ ሃስለር ይጠቀሳሉ፡፡ በእግርኳስ ዓለም ምርጡ ስፍራ ሴሪአው ነበር፡፡ የጣሊያን ክለቦችም ለቡድናቸው የሚመለምሉት ከደቡብ አሜሪካ እና አውሮፓ የተገኙ በጣም ምርጥ ተጨዋቾችን ብቻ ነበር፡፡ ዲያጎ ማራዶና፣ ካሬካ፣ ዚኮ፣ ሚሼል ፕላቲኒ፣ ማርኮ ቫንባስተን እና ሩድ ጉሊትን ለአብነት መጥቀስ ይቻላል፡፡ በዚያን ወቅት የጁቬንቱስ፣ ናፖሊ፣ ኤሲ ሚላን እናኢንተር ሚላን ተጨዋቾች ስም ዝርዝር ሲጠራ ሃሳባዊ የዓለም ምርጥ 11 ይመስላል፡፡ በዚያ ወርቃማ የእግርኳስ ዘመን የሀገሪቱ ነዋሪ በሙሉ የእግርኳስ ደጋፊ ይመስል ነበር፡፡ ስታዲየሞችም ቡድናቸው ሲያሸንፍ መመልከት በለመዱ ደጋፊዎች ጢም ብለው ይሞሉ ነበር፡፡ ጣልያን የእግርኳስ ገነት ነበረች፡፡ ሴሪአውም የዓለማችን ምርጡ ሊግ የሚል ስያሜ አግኝቶ ነበር፡፡

የከዋክብት ፍልሰት

ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ እውነታው የተገላቢጦሽ ሆኗል፡፡ በአሁኑ ወቅት በጣሊያን ክለቦች ከሚጫወቱ የውጭ ሀገር ተጨዋቾች መካከል ካርሎስ ቴቬዝ እና ፈርናንዶ ሎሬንቴ ላቅ ያለ ዝና አላቸው፡፡ አንዳቸውም ግን በመጪው ክረምት በሚደረገው የዓለም ዋንጫ ሀገራቸውን ወክለው ስለመጫወታቸው በእርግጠኝነት መናገር አይችሉም፡፡ አሁን አሁን ኮከብ ተጨዋቾች በሴሪ አው አይማረኩም፡፡ በዚያ እየተጫወቱ ያሉትም ለመልቀቅ ፅኑ ፍላጎት አላቸው፡፡
ከኤሲ ሚላን ጋር ለረዥም ጊዜ የዘለቀ ግንኙነት ያለው ካካ ሪያል ማድሪድን ለቅቆ ሚላንን ዳግመኛ ለመቀላቀል በዓመት ያገኘው ከነበረው 10 ሚሊዮን ዩሮ ከፍተኛ ቅነሳ አድርጎ በዓመት 4 ሚሊዮን ዩሮ ብቻ እየተከፈለው ለመጫወት ተስማምቶ ነበር፡፡ ነገር ግን ደመወዙ አሁንም ዳግም ቅነሳ ሊደረግበት የመሆኑ ነገር አልተዋጠለትም፡፡ በቅርቡ ወደ ፍሎሪዳ ማምራቱ አይቀሬ መሆኑም እየተነገረ ነው፡፡

ከ1994 እስከ 2003 ባለው ጊዜ ውስጥ ለአውሮፓ እግርኳስ ማህበረሰብ ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ መድረስ የቻሉ የጣሊያን ክለቦች 17 ናቸው፡፡ በአንፃሩ ግን ከ2004 እስከ 2013 ባለው ጊዜ ውስጥ ሩብ ፍፃሜውን መቀላቀል የቻሉት አምስት ብቻ ናቸው፡፡ ይህም የጣሊያን እግርኳስ ምን ያህል እንደተቀዛቀዘ አመላካች ነው፡፡ ‹‹በሌሎች የአውሮፓ ሀገራት ያለው የእግርኳስ ፍጥነት በጣሊያን ጨዋታው ከሚካሄድበት ፍጥነት የተለየ ነው›› በማለት የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ቼዛሬ ፕራንዴሊ በቅርቡ ሲማርሩም ተደምጧል፡፡ በርካታ ታዛቢዎች በሀገሪቷ የሚከናወኑ የእግርኳስ ጨዋታዎችን ደረጃ ከግምት ውስጥ በማስገባት በጨዋታ ዕለት ደጋፊዎች ምን እንደሚውጣቸው ይጠይቃሉ፡፡ ብዙውን ጊዜ ጨዋታዎች የሚደረጉት አብዛኛዎቹ መቀመጫዎች ሰው አልባ በሆኑ ስታዲየሞች ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ ባለፉት ሁለት ዓመታት የሚላን ደር አሊያም ጁቬንቱስ ከኤሲ ሚላን ባደረጉት ጨዋታ እንኳን ትኬቶች ሙሉ በሙሉ አልተሸጡም፡፡ በእነዚህ ዓመታት ጁቬንቱስ ከኤሲ ሚላን ያደረጉትን ጨዋታ በአማካይ 44 ሺ ተመልካቾች ተመልክቶታል፡፡ የቦሩሲያ ዶርትሙንድን ጨዋታ የሚከታተሉ ተመልካቾች ቁጥር ግን የዚህን እጥፍ ይሆናል፡፡

ኢንቨስተሮች በጥብቅ ይፈለጋሉ

በአንድ ወቅት በእግርኳስ አብዳ በነበረችው ሀገር የክለብ ባለቤቶች እያደር ነጭናጮች ሆነዋል፡፡ በከፍተኛ ዕዳ ተዘፍቀው እና ተበሳጭተው ምንም አይነት የተለያዩ የዕድገት ስትራቴጂ ሳይዙ እንዳው በደመነፍስ ከአንዱ ስምምነት ወደ ሌላው ለዓመታት ሲቅበዘበዙ ከርመዋል፡፡ እያንዳንዱ የውድድር ዘመን ባለፈ ቁጥርም እራሳቸው በፈጠሩት ችግር ይሰቃያሉ፡፡ አሁን አሁን ግን ቡድናቸው በችግር ውስጥ ሲሆን ዝምታን መምረጥ ትተዋል፡፡ እንዳውም ያለምንም ፍርሃት ክለቡን መግዛት የሚፈልግ ካለ ቡድኑ ለሽያጭ እንደሚቀርብ ይናገራሉ፡፡ አሊያም ደግሞ ለጊዜውም ቢሆን ሸሪክ ሊሆን የሚችል የፈረጠመ የፋይናንስ አቅም ያለው ወገን ያፈላልጋሉ፡፡

ከሁለት ዓመት በፊት ኤንሪኮ ፕሬዚዩሲ ‹‹ጄኖዋን ለመግዛት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ሊያነጋግረኝ ይችላል›› ሲሉ ከ1 ሚሊዮን ዩሮ ባነሰ ገንዘብ የግላቸው ስላደረጉት ክለብ ተናግረዋል፡፡ ማሲሞ ቼሊኖ በበኩላቸው የሰርዲኒያውን ክለብ ካግሊያሪ ካልቺዮ ለአንድ ሼክ አሳልፈው ለመሸጥ ተነሳስተው ነበር፡፡ ፍላጎታቸው አሁን ተቀዛቅል፡፡ ነገር ግን በአንድ ወቅት የሚዲያዎች ትኩስ ወሬ የነበረ እና አሁንም ድረስ በደጋፊዎች አዕምሮ ውስጥ የሚመላለስ ነው፡፡ የኢንተር ሚላኑ ፕሬዝዳንት ማሲሞ ሞራቲም ቢሆኑ ከ2011 ጀምሮ ገዢ ሲያፈላልጉ ነበር፡፡ በለስ ቀንቷቸውም ባለፈው ዓመት በክለቡ ከነበራቸው ድርሻ 75 በመቶ ያህሉን ኢሪክ ቶሂር ለተባሉ ኢንዶኔዢያዊ ባለሀብት በ250 ሚሊዮን ዩሮ ሸጠዋል፡፡ ሞራቲ በፕሬዝዳንትነት ባለፉባቸው 18 ዓመታት የተቆለለውን የክለቡን ዕዳ በሂሳብ መዝገብ ላይ ለማስተካከል በማሰብ እየተመናመነ ከመጣው የቤተሰባቸው ሀብት ከ1.2 ሚሊዮን ዩሮ በላይ ወጪ በማድረግ ክለቡ ላይ አፍስሰዋል፡፡ አሁን ደግሞ የክለብ ባለቤቶች ቁንጮ የሆኑት የኤሲሚላኑ ሲልሲዮ ቤርሎስኮኒ ክለቡን ለመልቀቅ እየተዘጋጁ ነው፡፡

‹‹በየዓመቱ 50 ሚሊዮን ዩሮ ከሚላን ጋር እከሰራለሁ ሲሉም ከጥቂት ቀናት በፊት ለጋዜታ ዴሎ ስፖርት ተናግረዋል፡፡ ቤርሎስኮኒ በታክስ ማጭበርበር እና ሌሎች ጥሰቶች ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው ወደ 100 ሚሊዮን ዩሮ ገደማ እንዲከፍሉ ተበይኖባቸዋል፡፡ ሞንዳደሪ ፐብሊሺንግ ግሩፕ የተባለው ድርጅታቸውም ለከፍተኛ ኪሳራ ተጋልጧል፡፡ ለቀድሞዋ ባለቤታቸው ቬሮኒካ ላሪዬም በቀን ወደ 50 ሺ ዩሮ ተቆራጭ እንዲያደርጉም ውሳኔ ተላልፎባቸዋል፡፡

በ1986 ቤርሎስኮኒ ኤሲ ሚላንን ሲረከቡ እንዲህ አይነቱ ጥብቅ ቁጥጥር አልነበረም፡፡ እርሳቸው እና ጓደኛቸው እንደዚሁም የክለቡ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት አድሪያኖ ጋሊያኒ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በክለቡ ላይ አፈሰሱ፡፡ በጄናሮ ጋቱሶ፣ አንድሪያ ፒርሎ፣ ካካ፣ ፓውሎ ማልዲኒ፣ አሌሳንድሮ ኔስታታ ሊዮናርዶ፣ ፊሊፖ ኢንዛጊ እና ክላረንስ ሲዶርፍ የተዋወቀር ቡድን በቤርሉስኮኒ ድጋፍ ጎመራ፡፡ የ77 ዓመቱ አዛውንት አሁን ላይ ሆነው በኃላፊነት ዘመናቸው በግትርነት ሊቀበሏቸው ያልፈለጓቸውን ሀሳቦች መለስ ብለው ማስታወሳቸው የማይቀር ነው፡፡ ለክለቡ የራሱ የሆነ ስታዲየም አለማስገንባታቸው፣ የራሳቸውን ትሩፋት ሳያኖሩ ማለፋቸው እና የታዳጊዎችን አካዳሚ በተገቢው መጠን አለመደገፋቸው ሳይፀፅታቸው የሚቀር አይመስልም፡፡

ሴሪ አው መሸጋሪያ ብቻ ነውን?

ከአባቷ ኃላፊነቱን የምትረከብ ከሆነ ከላይ የተጠቀሱት እንከኖች ለባርባራ ቤርሎስኮኒ ህይወትን አስቸጋሪ ያደርግበታል፡፡ ኤሲ ሚላን ስኳዱን ለማጠናከር በቀላሉ ቼክ መፃፍ እንደማይችል ታውቃለች፡፡ ታዳጊዎችን በማጎልበትም ቢሆን ፍሬያማ ለመሆን ጊዜ እንደሚጠይቅ ትገነዘባለች፡፡ ቢያንስ ለሶስት ዓመታት ከወጣት ማዕከሉ የሚወጡ ተጨዋቾች በዋናው ቡድን ላይ ተፅዕኖ መፍጠር እንደማይችሉም ግንዛቤው አላት፡፡ ይህም ሚላን ከማሪዮ ባሎቴሊ በስተቀር በክለቡ ያደገ ተጨዋች በሌለበት በማንሰራራት ላይ ያለውን ጁቬንቱስ እንዲከተል ያስገድደዋል፡፡
መልካሙ ነገር ሚላን ወጪውን ከገቢው ለማስተካከል ሙከራ ያደርግ የነበረ መሆኑ ነው፡፡ ባለፉት 10 ዓመታት በተጫዋቾች ዝውውር ሂደት ያስመዘገበው 16 ሚሊዮን ዩሮ ኪሳራ በንፅፅር ትንሽ ሊባል የሚችል ነው፡፡ ይበልጥ ግልፅ ለማድረግ ለንፅፅር ባርሴሎናን ማቅረብ እንችላለን፡፡ የካታላኑ ክለብ ባለፉት 10 ዓመታት ለተጫዋቾች ዝውውር ከ300 ሚሊዮን ዩሮ በላይ ወጪ አድርጓል፡፡ ይህ የገንዘብ መጠን ተጨዋቾችን ሸጦ ካገኘው ገንዘብ እጅግ የላቀ ነው፡፡ ‹‹ከስፔን አልያም ከእንግሊዝ ክለቦች ጋር ሲነፃፀር የጣሊያን ክለቦች ያለባቸው ዕዳ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ ይህ ደግሞ መልካም ነገር ነው›› ሲል የቀድሞው የኤሲሚላን አማካይ እና የጣሊያን እግርኳስ ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት ዴሜትሪዮ አልበርቲኒ ተናግሯል፡፡ ‹‹ምን መሆን እንደምንፈልግ መወሰን አለብን፡፡ ለሌሎች ሊጎች ተሰጥኦን አጎልብተን የምናበረክት ወይስ ራሳችን የትልቅ ሊግ ባለቤት መሆን የምንችል?›› ሲልም ሀሳቡን በግልፅ ያስቀምጣል፡፡

የለውጥ አየር እየነፈሰ ነው

እንደ ቤርሎስኮኒ ሁሉ ከ1986 ጀምሮ በእግር ኳሱ ኢንዱስትሪ ውስጥ የነበሩት የዩዲኔዜ ባለቤት ጂያንፓውሎ ፓዞ የኢኮኖሚው ቀውስ እንዳለ ሆኖ ትርፍ የሚያገኙበትን መንገድ አግኝተውታል፡፡ ክለባቸው ታዳጊ ተጨዋቾችን ከውጪ በማምጣት አጎልብቶ በከፍተኛ ትርፍ አሳልፎ ይሸጣቸዋል፡፡ ከጥቂት ዓመታት በፊት ፓዞ የስፔኑን ግራናዳ እና የእንግሊዙን ዋትፎርድ እግርኳስ ክለብንም የግላቸው አድርገዋል፡፡ የፋይናንሱ ሁኔታ ጥሩ ባልሆነበት በዚህን ወቅት ትርፍ ማስመዝገብ የቻለው ሌላኛው ክለብ ጁቬንቱስ ነው፡፡ ለዚህም ትልቁን ድርሻ የሚወስደው የራሱ ስታዲየም ባለቤት መሆኑ ነው፡፡ በመላው ሀገሪቱ በአቅራቢያው ባለ የመንግስት መስተዳድር ያልተያዘ ብቸኛው ስታዲየም ነው፡፡ የዋና ከተማዋ ክለብ ሮማም ተመሳሳይ የሆነ ገድል ለመፈፀም ተነሳስቷል፡፡ በዚህ ዓመት የአዲሱን ስታዲየም ግንባታ ይጀምራል ተብሎም ይጠበቃል፡፡ በ2016/17 የውድድር ዘመን አገልግሎት መስጠት ይጀምራል የሚል ግምት አለ፡፡ በጣልያን የሚገኙ የክለብ ባለቤቶች ወዴት ማምራት እንደሚፈልጉ ሀሳቡ ያላቸው ይመስላል፡፡ በሚሊዮኖች የሚከፈላቸው ከዋክብት ዘመን አልፏል፡፡ በመጪው ዘመን የዜና ርዕስ የሚሆኑት የእግርኳሱን ዓለም ለመቆጣጠር ከፍተኛ ፍላጎት ያላቸው በክለቦቻቸው ያደጉ ወጣቶች ናቸው፡፡

Health: በእርግዝና ወቅት የሚፈጠር የሰውነት መለጠጥ ከወሊድ በኋላ ቋሚ ሆኖ እንዳይቀር 3 ዘዴዎች

$
0
0

pregnancy-facts04 በእርግዝና ወቅት የሚፈጠርብኝ የሰውነት መለጠጥ ቋሚ ምልክት እንዳያመጣብኝ ምን ላድርግ?

ጥያቄ፡- የማቀርበው ጥያቄ የ28 ዓመት ወጣት ነኝ፡፡ የዛሬ ዓመት የምወደውን ሰው አግብቼ አብሬ መኖር ጀምሬያለሁ፡፡ አሁን ደግሞ ልጅ የመውለድ ፕሮግራሜን እውን ለማድረግ እፈልጋለሁ፡፡ እናት መሆን በጣም የሚያስደስት ልምድ እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ በማረግዝበት ጊዜ ግን በእርግዝና ወር የሚፈጠረው የሰውነት መለጠጥ ቋሚ ምልክት እንዳያመጣ መከላከል እፈልጋለሁ፡፡ ምን ባደርግ ይሻለኛል?
ራሄል ወሰኑ

ውድ ራሄል፡- መልካሙ ዜና በእርግዝና አልያም በከፍተኛ የክብደት መቀነስ ምክንያት የሚከሰተው ሸንተረር ማጥፋት አስቸጋሪ በመሆኑ ሳይጀመር በፊት መከላከል መፈለግሽ ነው፡፡ ቆዳ ላይ የሚታየው ቀላ ያለ ትንሽ ቆይቶ አንፀባራቂ ወይንም ብራማ ቀለም ያለው ምልክት ወንድ ሴት ሳይል ማንኛውም የሰውነት ክፍል ላይ ሊወጣ ይችላል፡፡ ለምሳሌ በሆድ፣ በችን፣ በጡት፣ በታፋ ወይም በታችኛው ወገን ላይ ሊታይ ይችላል፡፡ ከላይ ከተጠቀሱት ምክንያቶች በተጨማሪ ለተለያዩ ምክንያቶች በምንወስዳቸው መድሃኒቶች ምክንያት ጭምር ሊመጣ ይችላል፡፡
ሸንተረርን ለመከላከል የሚቻልባቸው ጥቂት መንገዶች መካከል የሚከተሉትን ልጠቁምሽ እወዳለሁ፡፡

1. ዘይት፣ ቅቤ፣ ሎሽን፣ ክሬም ወይም ለሸንተረር ተብለው የተሰሩ ልዩ ቅባቶችን ለቆዳችን የሚስማማውን በመምረጥ ሁሌም ያለመሰልቸት መቀባት፡፡ እርጉዝ ሴት ምንም አይነት ነገር ከመጠቀሟ በፊት ሐኪሟን ልታማክር የሚገባት ሲሆን ለጤናዋ የማይጎዳ መሆኑን ካረጋገጠች በኋላ በተፈገለው መጠን ያለማቋረጥ መቀባት ይኖርባታል፡፡
2. ‹‹ውሃ ጠጪ›› የሚባለው ተደጋጋሚ ምክር ለቆዳችን ጤናና ውበት በተራ ቁጥር አንድ ላይ ከሰፈረ ከርሟል፡፡ በመሆኑም ሸንተረር ከመከላከያ ዘዴዎች አንዱ ብዙ ውሃ መጠጣት መሆኑ ታምኖበታል፡፡ በቂ ውሃ ቆዳን በማለስለስ ሸንተረር በቆዳችን ላይ የመታየቱን እድል ዝቅ እንደሚያደርግ ጥናቶች የሚጠቁሙ ሲሆን፤ በብዛት የቡናና ሻሂ ተጠቃሚ የሆኑ ሰዎች የጠጡትን ያህል ወይም ከዛ በላይ ውሃ በላዩ ላይ ቢወስዱበት ሸንተረርን ለመቀነስ እንደሚችሉ ታውቋል፡፡

3. አትክልትና ፍራፍሬዎች በብዛት መመገብ

በሰለጠነው ዓለም ሰዎች ሸንተረርን ለማጥፋት ቀዶ ጥገና የሚያከናውኑ ሲሆን ውጤቱ በግለሰቡ ዕድሜ፣ የቆዳ አይነት እና የምግብ አወሳሰድ ይለያያል፡፡ በሀገራችን ይህንን መንገድ ተጠቅሞ ማስወገድ ስላልተለመደ ከላይ በተጠቀሱት ሁለት መንገዶች ተጠቅሞ መከላከል ይመረጣል፡፡ መልካሙን ሁሉ በእናትነትሽና በእርግዝናሽ መልካሙን ሁሉ እመኝልሻለሁ፡፡


የማለዳ ወግ …ዞን 9 ኞችን አደግፋለሁ !አግብቷቸው ስለጦመሩ መብታቸው መገፈፍ የለበትም (ነቢዩ ሲራክ)

$
0
0
ነቢዩ ሲራክ
የማለዳ ወግ …ዞን 9 ኞችን አደግፋለሁ !
አግብቷቸው  ስለጦመሩ መብታቸው መገፈፍ የለበትም  !

zone 9999 ዞን 9 ኞችን አከብራቸዋለሁ ፣ እዎዳቸዋለሁ!” የሃገር የህዝባችን ጉዳይ ያገባናል !” በሚል በፖለቲካ ፣ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ህይዎታችን ዙሪያ የሚያቀርቧቸው መጣጥፎች አስተማሪ ለመሆናቸው እማኝ ነኝ  !  ጦማርያኑ ቀፍድዶ ከያዘን ፍርሃት ወጥተን ህገ መንግስቱን መሰረት በማድረግ ለመብታችን እንድንተጋ ማነቃቃታቸው ቢያስመሰግን እንጅ የሚያስኮንን ፣ የሚያስወግዝ ፣ ብሎም ወህኒ የሚያስወርድ ነው አልልም።

ዞን 9 ኞችን የምንወድ የምንደግፍ  እኔና እኔን መሰሎች ጥቂቶች አይደለንም ። እልፍ አእላፎች ነን ። ቢያንስ እኔ በግል የወጣት ጦማርያኑ እንግልትና ጉዳት የሃገር  ጉዳት ነው ብየ አምናለሁ ። እልፍ  አእላፎች ጦማሪዎች ” ህገ መንግስቱን አልጣሱም “ስንል  ” ህገ መንግስቱ ይከበር ፣ ዞን 9ኞች ይፈቱ !” ዘንድ ድምጻችን ከፍ አድርገን እናሰማለን  !

የዞን 9 ጦማርያን የመጻፍ የመናገር መብታቸውን ተጠቅመው ተደራጅተው በሰለጠነና በዘመነ አካሔድ ፍርሃት ዝምታችን ሰብረውልናል።ስለዚህም የሃገርና የህዝብ ድንቅ ልጆች እንጅ በጠላትነት ሊፈረጁ አይገባም። “የህዝብ የሃገር ጉዳይ ያገባናል!” ብለው ግንባራቸውን ለመስዋዕት የሰጡት ወጣቶች የህግ ከለላ ያስፈልጋቸዋል እንጅ ህግ እየተሸራረፈ መብታቸው መጣስ የለበትም።

ዞን 9 ኞች የማይወዷቸው የማግፈልጓቸው ” ሃገርና ህዝብ በድለዋል ፣ በብዕራቸው ሰላም አደፍርሰዋል!” ካሉ  የተጨበጠ መረጃ ይዘው አይሞግቷቸው አልልም። ጉዳያቸው በህግ ማዕቀፍ ተመርምሮ እና የዋስ መብታቸው ተከብሮ ትክክለኛ ፍትህን ሊያገኙ  ይገባል። ይህ ሳይደረግ የሳሾቻቸው አቤቱታ ብቻ እየተሰማ ፣  ባልረባባ ምክንያት እየወነጀሉ ዞን 9ኞችን ሊያዳክሙና ከአደባባይ መድረኩ ሊያጠፏቸው አይገባም ።

በዚህ ረገድ የፍትህ አካላት የሃገርንና የህዝብን ደህንነት ከማስጠበቁ ባልተናነሰ  የታዳጊ ወጣት ጦማሪዎችን መብት የማስጠበቅ ሰው የመሆን የሞራል ግዴታ አለባቸው  !

“የህዝበና የሃገር ጉዳይ ያገባናል!” ያልን ፍዳችን በዝቷል ። ያም ሆኖ ዝም አንልም ፣ ያገባናልና በአደጋ ተከበን እንጦምራለን  !  አዎ  ! ያገባናልና !

ሰላም …

ነቢዩ ሲራክ

Sent from Samsung Mobile
zone-9-300×300.jpg

“የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ጥያቄ ፍትሐዊና ሕጋዊ ነው”

$
0
0

ሰንደቅ ጋዜጣጋዜጣው ሪፖርተር

አቶ አባዱላ ገመዳ

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈጉባዔ

 በአዲስአበባ ዙሪያያሉትን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ውስጥ የሚተዳደሩ ከተሞችን ከአዲስአበባ ጋር በማስተሳሰር በጋራ ለማልማት የወጣውን የተቀናጀ መሪዕ ቅድ በመቃወም ሰሞኑን በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች የተካሄደው ተቃውሞ ተከትሎ በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል። በአዳማ፣ በድሬዳዋ፣ በጅማ፣ በመደወላቡ፣ በአምቦ፣ በሐሮማያ ዩኒቨርሲቲዎችና በጠቅላላው በ11 ዩኒቨርሲቲዎች የተቀጣጠለው ተቃውሞ መነሻው የአዲስአበባና የፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ ማስተር ፕላን ትግበራ ጉዳይ ነው። ዕቅዱ “የኦሮሚያ ከተሞችን በመቁረስ ወደአዲስአበባ ለማጠቃለል የታቀደ ነው፣ በርካታ ኦሮሞዎች ከቤት ንብረታቸው ሊፈናቀሉ ነው” የሚሉ አስተያየቶች በተለይ በማህበራዊ ድረገጾች በስፋት በመሰራጨታቸው ተማሪዎች ግራ በመጋባት የወሰዱት እርምጃ እንደሆነ ይታመናል። መንግሥታዊ አካላትም በወቅቱ ሕዝቡን በማሳተፍ ስለፕላኑ (ዕቅዱ) በቂና ተከታታይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይቶችን አለማድረጋቸው ለግጭቱ መነሳት አንድ ምክንያት መሆኑ እየተነገረ ነው።

ቶ አባዱላ ገመዳ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈጉባዔ

ቶ አባዱላ ገመዳ
የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈጉባዔ

የመንግሥት ኮምኒኬሸን ጽ/ቤት ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ በመደወላቡ እና በአምቦ ዩኒቨርሲቲዎች ከተቃውሞው ጋር በተያያዘ 10 ሰዎች መሞታቸውን ይፋ ያደረገ ሲሆን በሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ እግርኳስ በመመልከት ላይ ባሉ ተማሪዎች ላይ ባልታወቁ ሰዎች በተወረወረ ፈንጂ 70 ያህል ተማሪዎች ሲቆስሉ አንድ ተማሪ መሞቱን አስታውቋል።

ጽ/ቤቱ በዚሁ የመንግሥትም አቋም በገለጸበት መግለጫው በፌዴራልና በክልል የፀጥታ ኃይሎች ትብብር ሁከቱ በተፈጠረባቸው ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ያለውን ሁኔታ ለማረጋጋት መቻሉን ጠቅሶ እስካሁን በተደረገው ማጣራት ከበስተጀርባ በመሆን ሁከቱን በማነሳሳትና በማቀነባበር ተግባር ላይ የተሰማሩት ጥቂት ፀረ ሰላም ኃይሎች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል ብሏል። ከዚሁ ግርግር በስተጀርባ የቆሙትና ከዚህ ቀደም በነበሩ ግጭቶች እጃቸውን ሲያስገቡ የነበሩ የአገር ውስጥና ከአገር ውጭ ያሉ ኃይሎች በሚቆጧጠሯቸው ሚዲያዎች እየታገዙ ይህንን የተማሪዎችን ጥያቄ ለጥፋት ዓላማቸው መጠቀሚያ ለማድረግ መንቀሳቀሳቸውን በመግለጫው አስታውቋል።

በተፈጠረው ሁከት ሳቢያ ጉዳት ለደረሰባቸውና ወገኖችና ቤተሰቦቻቸው መንግስት የተሰማውን ሐዘን የገለጸ ሲሆን የጥፋቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ የነበሩትን ተከታትሎ ለፍርድ ለማቅረብ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጧል።

በአዲስ አበባ ዙሪያ ያሉትን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ውስጥ የሚተዳደሩ ከተሞችን ከአዲስ አበባ ጋር በማስተሳሰር በጋራ ለማልማት የወጣውን የተቀናጀ መሪ ዕቅድ ጋር ተያይዞ በተማሪዎች ስለተነሳው ጥያቄና በመንግሥት ስለተወሰደው እርምጃ የአሜሪካ ድምጽ አማርኛ ክፍል የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈጉባዔ የሆኑትን አቶ አባዱላ ገመዳን ከትላንት በስቲያ አነጋግሯል። እንደሚከተለው ቀርቧል።

ጥያቄ፡- ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ብዙ ሰዎች ሞተዋል። ሰልፉ የተካሄደው ባልታጠቁ ተማሪዎች ነው። በሮቤ፣ በአምቦ፣ በጅማ፣ በነቀምት፣ በመዳወላቡ፣ ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል። መንግሥትም ራሱ ሐሙስ ዕለት ባወጣው መግለጫ እስከ 10 ሰዎች መገደላቸውን አምኗል፣ በዚህ ላይ የሚሰጡን ምላሽ ምንድነው?

አቶ አባዱላ፡- እውነት ነው፤ በኦሮሚያ ክልል ባሉት ዩኒቨርሲቲዎች የተነሳ የተቃውሞ ጥያቄ አለ። ጥያቄው የተነሳው በኦሮሚያና የአዲስ አበባ የጋራ ማስተር ፕላን በሚመለከት የተነሳ የተቃውሞ ጥያቄ ነው። በሁሉም አካባቢ ተማሪዎች ያነሱት ጥያቄ ፍትሃዊና ሕጋዊ ነው። እነዚህን ፍትሃዊና ሕጋዊ ጥያቄ በየአካባቢው ያሉት፣ የዩኒቨርሲቲ አስተዳደርም ሆነ በየአካባቢው ያሉት አስተዳደሮች ለመመለስ ጥረት አድርገዋል። ጉዳዩን በቅርበት ይከታተሉ የነበሩ የመንግሥት ኃላፊዎችም በጉዳዩ ሒደት ላይ ማብራሪያ ለመስጠት ሞክረዋል። ይሁንና አንዳንድ ቦታ ተማሪዎቹ ጠየቁ፣ በቂ መልስ አላገኘንም አሉ። ለበላይ አካልም ጥያቄያቸው እንዲሄድላቸው ጠየቁ፣ ግን ደግሞ ያ-ምላሽ ከመምጣቱ በፊት ነው ሰልፍ ወጡ። እንግዲህ ሰላማዊ ሰልፍ የመውጣት ሕገ-መንግሥታዊ መብት ነው። ይህ በሕገ-መንግስቱ የተቀመጠ ነው። ይሄ እንደተጠበቀ ሆኖ ሠላማዊ ሰልፍ ሲወጣ አስቀድሞ ማሳወቅ እንደሚገባ ይደነግጋል። ይሄ የሚሆነው በአካባቢው ያለ የመንግሥት አስተዳደር ሰልፍ የወጣው ሕዝብ አንድም ጉዳት እንዳይደርስበት ለመከላከል ነው። ሁለተኛ ደግሞ በሌላው ዜጋ ንብረትና ሐብት ጉዳት እንዳይደርስ ለመጠበቅ ነው። እነዚህ ሁለቱ ካልተሟሉ ችግር ሊከሰት እንደሚችል በአገራችንም በሌሎች ዴሞክራሲያዊና ባደጉ አገራትም ይታወቃል። መጀመሪያ ተማሪዎቹ ጥያቄያቸው ፍትሐዊ ሆኖ ሠላማዊ ሰልፉ ሕጉን ተከትሎ ያለማካሄድ ችግር ያጋጠመበትና ሳያሳውቁ በኃይል ስለተወጣ ከተማ ላይ በንብረት ላይ የደረሰ ኪሣራ አለ። ይሄ ወደባሰ ችግር እንዳይሰፋ የፀጥታ ኃይሎች ለመከላከል የወሰዱት እርምጃ አለ። የፀጥታ ኃይሎች አድማ ለመበተን ጢስ እና ውሃ ተጠቅመዋል። ይህን አልፎ ለሕይወት መጥፋትና ለሌሎችም ችግሮች የተከሰቱበት ሁኔታ አለ።

ጥያቄ፡- የተማሪዎቹ ጥያቄ ፍትሐዊና ሕጋዊ ነው ብለዋል። ሠላማዊ ሰልፍ ደግሞ በሕገመንግሥቱ የተቀመጠ መብት ነው ብለዋል። ሠላማዊ ሰልፍ ማድረግ የሚፈልግ ለመንግሥት አካላት ማሳወቅ ነው ብለዋል። ነገር ግን የታጠቁ ኃይሎች ልጆቹ ላይ ተኩስ እንደከፈቱና በዚህም ምክንያት የማይተካ ሕይወት እንደተሰዋ ነው የሚነገረው። ጥያቄያቸው ትክክለኛ እስከሆነ ድረስ ለዚህ ግድያ ምን መልስ ይሰጡናል?

አቶ አባዱላ፡- በመጀመሪያ ይህ መምጣት የሌለበት ነው። ሕይወትም ንብረትም መጥፋት በጣም የሚያሳዝን ነው። መንግሥትም ሐዘኑን ገልጿል። እኔም በቦታው ደርሼ አይቻለሁ፣ አዝኛለሁ። መሆን የማይገባው ጉዳይ ነው። በቦታው በኃይል ለመመለስ ወይም በጥይት ለመመለስ አይደለም ዝግጅቱ። አንድ ምሳሌ ለማንሳት ልሞክር። የአድማ በታኝ የፌዴራል ፖሊስ በቦታው የደረሰው ብዙ ተሽከርካሪዎችና ንብረት ከተቃጠለ በኋላ ማታ ላይ ነው። ማምሻውን 11 ሰዓትና ከዚያ በኋላ ነው የደረሰው። ቃጠሎው እየሰፋ ሲሄድ ነው፣ የክልሉ መንግሥት ይሄ ነገር የከፋ ሕይወት ሊያጠፋ ስለሚችል የሚቆጣጠር ኃይል መግባት አለበት ብሎ ለፌዴራል መንግሥት ጥያቄ አቅርቧል።

ጥያቄ፡- ተማሪዎቹ መኪናዎችን ሲያቃጥሉ ነበር ነው የሚሉኝ?

አቶ አባዱላ፡- እንግዲህ በአምቦ ከተማ ቀደም ሲል ሠላማዊ ሰልፍ ሲወጣ ማሳወቅ ይገባል ያልነው ባመፈፀሙ፣ ቅድመ ዝግጅት ባለመደረጉ፣ ተማሪዎቹ በግቢያቸው ውስጥ የመጨረሻውን ዝግጅት አድርገው የወጡ ቢሆንም፤ ከውጪ ግን ተማሪዎችን የተቀላቀለ ብዙ ኃይል አለ። የዘረፋ ፍላጎት ያለው፣ የማውደም ፍላጎት ያለው ኃይል ተቀላቅሏል። ከተቀላቀለ በኋላ ለምሳሌ በአምቦ አበበች መታፈሪያ የሚባል ሆቴል ተዘርፏል። ሆቴል ውስጥ የነበሩት የቱሪሰት መኪናዎች ተቃጥለዋል። እንደዚህም የኮንስትራክሽንና ቢዝነስ ባንክ ተቃጥሏል። የምዕራብ ሸዋ ፍ/ቤት ዶክመንቶችና ፍ/ቤቱ ራሱ ተቃጥሏል። እንዲያውም ተማሪዎች ናቸው ለማለት የማያስችለው ከጥበቃ ኃይሎች ትጥቅ በመቀበል ወደተኩስ የተገባበት ሁኔታ ነበር። ይሄ ነገር ሄዶ ሄዶ ብዙ ሕይወት፣ ብዙ ንብረት እንደሚያወድም ይታወቃል። መንግሥት ይህን የመቆጣጠር ኃላፊነት አለበት።

ትዴኢ አንድነትና መኢአድን ለመዋሐድ እየጣረ ነው ትዴኢ አንድነትና መኢአድን ለመዋሐድ እየጣረ ነው

$
0
0

በ  ዘሪሁን ሙሉጌታ /ሰንደቅ ጋዜጣጋዜጣ

የሰባት ፓርቲዎች ስብስብ የሆነው “ትብብር ለዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ” ወይም “ትብብር” የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እንዲዋሐዱ የመጨረሻ ጥረት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

የትብብሩ ሰብሳቢ አቶ ግርማ በቀለ ትናንት ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት “ትብብሩ” ሁለቱ ፓርቲዎች እንዲዋሐዱ ጥረት እያደረገ ያለው እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በጉጉት ሲጠብቀው የቆየው ውህደት ያለበቂ ምክንያት የመስተጓጎል አዝማሚያ በማሳየቱ ነው ብለዋል። በተጨማሪም ትብብሩ እንደባለድርሻ አካል ደግሞ በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል ያለው ልዩነት በሰላም ተጠናቆ ውህደቱ እውን ሆኖ የኢትዮጵያ ሕዝብ የውህደት ጥያቄ መልስ እንዲያገኝ የራሱን አዎንታዊ አስተዋፅኦ ለማድረግ ነው ብለዋል።

ትብብሩ ይሄንኑ ዓላማ ለማሳካት ከሁለቱም ፓርቲዎች ጋር ለመዋሐድ የውህደት ጥያቄ በደብዳቤ ማቅረቡን የገለፁት አቶ ግርማ የትብብሩ የመጀመሪያ ፍላጎት ሁለቱ ፓርቲዎች ውህደት ከተጠናቀቀ በኋላ ትብብሩ አዲስ ከሚፈጥረው ውህደት ጋር መልሶ መዋሐድ እንደሚፈልግ አስታውቀዋል።

ይሁን እንጂ በመኢአድና በአንድነት መካከል የሚደረገው ውህደት የማይሳካ ከሆነ ከሁለት አንዳቸው ጋር ለመዋሐድ መዘጋጀታቸውን የጠቀሱት አቶ ግርማ ወደዚህ ውሳኔ ከመምጣታቸው በፊት ግን የሶስትዮሽ ውይይት እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።

ፓርቲዎቹ ከመዋሐዳቸው በፊት የፓርቲዎች ርዕዮተ ዓለምና የአደረጃጀት ጥያቄዎች በምን መልኩ ማስታረቅ እንዲሚቻል የተጠየቁት አቶ ግርማ፤ ችግሩ የርዕዮተዓለምና የአደረጃጀት አለመሆኑን ገልፀዋል። እሳቸው የሚመሩት “ትብብር” በአራት የክልልና በሶስት ህብረብሔራዊ ፓርቲዎች የተዋቀረ መሆኑን በማስታወስ ከመኢአድም ሆነ ከአንድነት ጋር ሊያዋህዳቸው የሚችለውን መሠረታዊ መነሻ አጥንተው ማጠናቀቃቸውን አስረድተዋል። ያስቸገራቸው ግን የተዋሐደ ፕሮግራም ያላቸው መኢአድና አንድነት ለመዋሐድ አለመወሰናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል።

“የአንድነትና የመኢአድ ፕሮግራም ስታየው ሁለቱ ያልተዋሐዱ ማን ሊዋሐድ ይችላል የሚል ጥያቄ ያጭርብሃል” የሚሉት አቶ ግርማ ትብብሩ እንደተፈለገው የሚሳካ ከሆነ በቅርቡ የሶስትዮሽ መግለጫ እንደሚሰጡ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

ባለፈው ሰኞ የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት በዚሁ ጉዳይ ለመወያየት ኮረም ባለመሟላቱ ለመጪው ቅዳሜ ቀጠሮ መያዙ ለማወቅ ተችሏል። በመኢአድ በኩል እስካሁን የውህደት በሩ አለመዘጋቱን ለፓርቲው ቅርበት ያላቸው ወገኖች እየገለፁ ነው። ሆኖም “ትዴኢ” ወደ አንድነት እንዲገባ በትብብሩ ላይ ግፊት እያደረገ ነው በሚል ስማቸውን መግለፅ ያልፈለጉ የመኢአድ አመራሮች ስጋታቸውን ገልፀዋል።

“ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ” ወይም “ትብብር” ሰባት በብሔርና በህብረብሔር የተደራጁ በአመዛኙ በደቡብ ክልል የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች የተሰበሰቡትና በቅርቡም በይፋ መተባበራቸውን ያስታወቁ የፓርቲዎች ስብስብ መሆኑ አይዘነጋም።

የሰባት ፓርቲዎች ስብስብ የሆነው “ትብብር ለዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ” ወይም “ትብብር” የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እንዲዋሐዱ የመጨረሻ ጥረት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

የትብብሩ ሰብሳቢ አቶ ግርማ በቀለ ትናንት ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት “ትብብሩ” ሁለቱ ፓርቲዎች እንዲዋሐዱ ጥረት እያደረገ ያለው እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በጉጉት ሲጠብቀው የቆየው ውህደት ያለበቂ ምክንያት የመስተጓጎል አዝማሚያ በማሳየቱ ነው ብለዋል። በተጨማሪም ትብብሩ እንደባለድርሻ አካል ደግሞ በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል ያለው ልዩነት በሰላም ተጠናቆ ውህደቱ እውን ሆኖ የኢትዮጵያ ሕዝብ የውህደት ጥያቄ መልስ እንዲያገኝ የራሱን አዎንታዊ አስተዋፅኦ ለማድረግ ነው ብለዋል።

ትብብሩ ይሄንኑ ዓላማ ለማሳካት ከሁለቱም ፓርቲዎች ጋር ለመዋሐድ የውህደት ጥያቄ በደብዳቤ ማቅረቡን የገለፁት አቶ ግርማ የትብብሩ የመጀመሪያ ፍላጎት ሁለቱ ፓርቲዎች ውህደት ከተጠናቀቀ በኋላ ትብብሩ አዲስ ከሚፈጥረው ውህደት ጋር መልሶ መዋሐድ እንደሚፈልግ አስታውቀዋል።

ይሁን እንጂ በመኢአድና በአንድነት መካከል የሚደረገው ውህደት የማይሳካ ከሆነ ከሁለት አንዳቸው ጋር ለመዋሐድ መዘጋጀታቸውን የጠቀሱት አቶ ግርማ ወደዚህ ውሳኔ ከመምጣታቸው በፊት ግን የሶስትዮሽ ውይይት እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።

ፓርቲዎቹ ከመዋሐዳቸው በፊት የፓርቲዎች ርዕዮተ ዓለምና የአደረጃጀት ጥያቄዎች በምን መልኩ ማስታረቅ እንዲሚቻል የተጠየቁት አቶ ግርማ፤ ችግሩ የርዕዮተዓለምና የአደረጃጀት አለመሆኑን ገልፀዋል። እሳቸው የሚመሩት “ትብብር” በአራት የክልልና በሶስት ህብረብሔራዊ ፓርቲዎች የተዋቀረ መሆኑን በማስታወስ ከመኢአድም ሆነ ከአንድነት ጋር ሊያዋህዳቸው የሚችለውን መሠረታዊ መነሻ አጥንተው ማጠናቀቃቸውን አስረድተዋል። ያስቸገራቸው ግን የተዋሐደ ፕሮግራም ያላቸው መኢአድና አንድነት ለመዋሐድ አለመወሰናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል።

“የአንድነትና የመኢአድ ፕሮግራም ስታየው ሁለቱ ያልተዋሐዱ ማን ሊዋሐድ ይችላል የሚል ጥያቄ ያጭርብሃል” የሚሉት አቶ ግርማ ትብብሩ እንደተፈለገው የሚሳካ ከሆነ በቅርቡ የሶስትዮሽ መግለጫ እንደሚሰጡ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

ባለፈው ሰኞ የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት በዚሁ ጉዳይ ለመወያየት ኮረም ባለመሟላቱ ለመጪው ቅዳሜ ቀጠሮ መያዙ ለማወቅ ተችሏል። በመኢአድ በኩል እስካሁን የውህደት በሩ አለመዘጋቱን ለፓርቲው ቅርበት ያላቸው ወገኖች እየገለፁ ነው። ሆኖም “ትዴኢ” ወደ አንድነት እንዲገባ በትብብሩ ላይ ግፊት እያደረገ ነው በሚል ስማቸውን መግለፅ ያልፈለጉ የመኢአድ አመራሮች ስጋታቸውን ገልፀዋል።

“ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ” ወይም “ትብብር” ሰባት በብሔርና በህብረብሔር የተደራጁ በአመዛኙ በደቡብ ክልል የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች የተሰበሰቡትና በቅርቡም በይፋ መተባበራቸውን ያስታወቁ የፓርቲዎች ስብስብ መሆኑ አይዘነጋም።

መድረክ በአዲስ አበባ ሠላማዊ ሰልፍ ጠራ

$
0
0

በ  ዘሪሁን ሙሉጌታ

medrekኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) በሀገሪቱ በሚታዩ ወቅታዊ ችግሮች ላይ መንግስት እየወሰደ ያለውን የኃይል እርምጃ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን አስታወቀ።

የመድረክ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጥላሁን እንዳሻው ትናንት ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት ሰላማዊ ሰልፉ በመጪው እሁድ ግንቦት 3 ቀን 2006 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑን አስታውቀዋል። የሰላማዊ ሰልፉ ዓላማ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚነሱ ሰላማዊ ተቃውሞዎች ላይ መንግስት የኃይል ምላሽ እየሰጠ በመሆኑና የፖለቲካ ምህዳሩም እየጠበበ በመምጣቱ መንግስት የዜጎችን ሕገ-መንግስታዊ መብቶች አክብሮ ተቃውሞዎችን በሰለጠነ አግባብ እንዲያስተናግድ ግፊት ለማድረግ ነው ብለዋል።

ከዚህ ጎን ለጎን በቀጣይ የፖለቲካ ምህዳሩ እንዲስተካከልና በመጪው ዓመት የምርጫ ዝግጅት ለማድረግ መንግስትን ለድርድር ዝግጁ እንዲሆን ለማስገደድ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ጥላሁን የሕዝብ መፈናቀልና በኦሮምያ አካባቢ የተነሱ ተቃውሞዎች መንግስት የሕዝብን ጥያቄ በቸልታ የማየት ውጤት መሆኑን ለመግለፅ ነው ሲሉ አስረድተዋል። በአጠቃላይ ሰልፉ ላይ የሰብአዊ፣ የዴሞክራሲ ጥያቄዎች ላይ የሚያተኩር እንደሆነም አስረድተዋል።

     ሰላማዊ ሰልፉን ለማካሄድ ሁለት አማራጮች ማቅረባቸውን አቶ ጥላሁን የገለፁ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ፓርቲው ዋና ጽ/ቤት ከሚገኝበት ስድስት ኪሎ ተነስቶ በፒያሳ በኩል ወደ ድላችን ሐውልት እንዲሁም ሁለተኛው አማራጭ ደግሞ ስድስት ኪሎ ከሚገኘው የመድረክ ዋና ጽ/ቤት ተነስቶ በቀድሞ ሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ አድርጎ በአራት ኪሎ አደባባይ በማለፍ ወደ መስቀል አደባባይ መሆኑን ተናግረዋል። ለሰላማዊ ሰልፉ እውቅና ለማግኘት ለአዲስ አበባ አስተዳደር በትናንትናው ዕለት የማመልከቻ ደብዳቤ መቅረቡንና ምላሽ ከአስተዳደሩ እየጠበቀ መሆኑን ጠቅሰዋል። ጎን ለጎን ሰልፉን የሚያደራጅ አካል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በሰልፉም ላይ እስከ 50 ሺህ ሰው እንደሚሳተፍ እንጠብቃለን ሲሉ ጨምረው ገልፀዋል።

ሰማያዊ ፓርቲ በተገደሉት ተማሪዎች ጉዳይ መግለጫ አወጣ፤ “የዜጎችን ጥያቄ በግድያ ማስቆም አይቻልም”

$
0
0

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ነጻ እንዲወጡ እገዛ ያደረገችላቸውን ጨምሮ አብዛኛዎቹ አገራት የህዝብን ጥያቄ በተገቢው የሚያዳምጡ፣ ችግሮች ሲኖሩ በጠረጴዛ ዙሪያና በሰከነ መልኩ መፍታት የሚችል መንግስት መመስረት ሲችሉ በተቃራኒው በአገራችን ስልጣን ላይ ያለው ህወሓት/ኢህአዴግ ግን ዜጎችን በኃይል እየገዛ ይገኛል፡፡ ለዚህም በቅርቡ በአገራችን የተለያዩ ክፍሎች የተፈጸሙትን ግድያዎችና ሌሎች ህገ ወጥ እርምጃዎች በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል፡፡

የአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙት ከተሞች ‹‹የተቀናጀ መሪ ፕላን (ማስተር ፕላን)›› አስመልክቶ በስርዓቱ ላይ ጥርጣሬ የገባቸው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ያነሱት ሰላማዊ ጥያቄ ተከትሎ በርካታ ተማሪዎችና ነዋሪዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ብዙዎቹ ቆስለዋል፡፡ በርካታ ተማሪዎች ለእስር ተዳርገዋል፡፡ በተያያዘ ከወራት በፊት በሀረር ከተማ የተከሰተውን ቃጠሎ ተከትሎም ዜጎች ላይ ተመሳሳይ እርምጃ ተወስዷል፡፡ በተመሳሳይ በባህር ዳርና ጎንደር ከተሞች ‹‹ህገ ወጥ ግንባታ ነው›› ተብለው ያለ ካሳ፣ ቅያሬና በቂ ጊዜ ቤታቸው የፈረሰባቸው ዜጎች ቤታቸው በዚህ ሁኔታ መፍረሱ አግባብ አለመሆኑን በመግለጻቸው በጥይት ተደብድበዋል፡፡ አብዛኛዎቹም ለከፋ ድብደባ ተዳርገዋል፡፡ ቀሪዎቹ በተለይም ጥያቄ ያነሳሉ ተብለው የተፈሩት አባወራዎች እስር ቤት ውስጥ ታጉረዋል፡፡
tplf killing ethiopians
ዜጎች ጥያቄያችው ምንም ይሁን ምን ‹‹መንግስት ነኝ!›› ብሎ ስልጣን ላይ የተቀመጠ አካል ጥያቄያቸውን አዳምጦ በሰከነ መንገድ ምላሽ ወይንም መፍትሄ የመስጠት ግዴት የነበረበት ቢሆንም ዜጎችን ምንም አይነት ጥያቄ እንዲያነሱ የማይፈልገው ገዥው ፓርቲ ምላሹ ለሰላማዊ ዜጎች የማይገባ ጥይት ሆኗል፡፡ ገዥው ፓርቲ የዜጎችን ጥያቄ በኃይል ለማፈን የሚሞክረው ለዜጎች መሰረታዊ ጥያቄን አሟልቶ አገር የመምራት ብቃት የሌለው ከመሆኑ አንጻር ህዝብ ሌሎች በርካታ ጥያቄዎችን ያነሳብኛል ብሎ ስለሚሰጋ፣ የተነሱትንም ጥያቄዎች የመመለስ አቅም ስለሌለውና ምንም አይነት ችግር ቢኖርም ህዝብ እያስፈራራ ለመግዛት ካለው አባዜ ነው፡፡

ይህ ስርዓቱ የራሱን መሰረታዊ ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ መመለስና መፍታት ሲያቅተው ህዝብን በኃይል አፍኖ የመግዛት የፖለቲካ ባህሉም አገራችን ከመቼውም ጊዜ በላይ ወደ በፖሊስ መንግስትነት (ፖሊስ ስቴት) ስር እንደወደቀች ዋነኛ ማሳያ ነው፡፡ በዚህ የስርዓቱ ባህሪ ምክንያት ኢትዮጵያ አገራችን ዜጎች ሰላማዊ ጥያቄያቸውን ለመንግስት የማያቀርቡባት፣ ጥያቄያቸውን ሲያቀርቡም ህይወታቸውን የሚያጡባት አገር እንደሆች የሰሞኑ አረመኔያዊ እርምጃን በምሳሌነት ማንሳት ይቻላል፡፡

ዜጎች የትኛውንም ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ማንሳት መብታቸው እንደሆነ የሚያምነውና ለዚህም የሚታገለው ሰማያዊ ፓርቲ ስርዓቱ በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች እየፈጸማቸው የሚገናቸውን አረመኔያዊ እርምጃዎች ያወግዛል፡፡ እስካሁን ድረስ ገዥው ፓርቲ በኢትዮጵያውያን ላይ የወሰደውን እርምጃ ህጋዊ ለማስመሰል የባንክ ዘረፋንና ህገ ወጥ የቤት ግንባታን የመሳሰሉትን ምክንያቶች በመጥቀስ የተወሰደውን እርምጃ ህጋዊ ለማድረግ መሞከሩም ተጠያቂነት የጎደለውና ከምክንያት የራቀ በመሆኑ፤ እነዚህ ዜጎች ላይ የተወሰደውን እርምጃ ላይ ለህዝብ በቂ መረጃ እንዲሰጥና ተጠያቂነቱን እንዲወስድ እናሳስባለን፡፡
ህወሓት/ኢህአዴግ የአገራችንን ህዝብ ጥያቄ በኃይል ለመደፍጠጥ ቆርጦ የተነሳ በመሆኑ የትኛውንም ሰላማዊ ጥያቄ ያነሳ ኢትዮጵያዊ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ እንደሚወስድ በተደጋጋሚ ታይቷል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያውያን ገዥው ፓርቲ በፈጠረው የከፋፍለህ ግዛ ስርዓት ሳይወናበዱ በዜጎቻችን ላይ የሚደርሰውን ህገ ወጥ እርምጃ ላይ ድምጻቸውን እንዲያሰሙና ለስርዓቱ መሳሪያ ከመሆን እንዲቆጠቡ እንዲሁም አገር በቀልና ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተቋማት፣ የሚዲያ ተቋማት፣ የፖለቲካ ድርጅቶችና ሚዲያዎች ገዥው ፓርቲ በህዝብ ላይ እየወሰደው ያለውን የኃይል እርምጃ እንዲያጋልጡና እንዲቃወሙ፣ እያጋለጡና እየተቃወሙ ያሉትም አጠናክረው እንዲቀጥሉ ሰማያዊ ፓርቲ ያሳስባል፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
ሰማያዊ ፓርቲ
ሚያዝያ 2006 ዓ.ም

የፊታችን እሁድ ሜይ 11 የሚኒሶታውን መድሃኔዓለም ቤ/ክ የወደፊት እጣ ይወስኑ

$
0
0

ለሰላም እና ለአንድነት የቆሙ ምዕመናን ያስተላለፉት ጥሪ። የፊታችን እሁድ የሚኒሶታውን ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ የወደፊት እጣ ለመወሰን፣ አዲስ የቦርድ አባላትን ለመምረጥ ጥሪ ቀርቧል። አባል የሆናችሁ እንድትገኙ ይላል ጥሪው። በራሪ ወረቀቱ የሚከተለው ነው።10262114_10203695584260967_6020887796663799937_n

በእውቀቱ ስዩም ስለ ዞን 9 ጦማሪዎች፤ “የመከራችሁ ተካፋይ ባለመሆኔ ሐፍረቱን አልችለውም”

$
0
0

Bewketu Seyoum – Hagere Mariam (Maryland) USA [Must Listen)ታዋቂው የስነጽሁፍ ሰውና ኮሜዲያን በእውቀቱ ስዩም በፌስቡክ ገጹ በእስር ላይ ስለሚገኙት የዞን 9 ጦማሪያን የሚከተለውን አስፍሯል።

ነጻነትና ፍትህ በሌሉበት አገር ውስጥ የልማት አውታሮችን መገንባት የት ለመድረስ ነው?የባቡር ሀዲድ ግንባታ ሳይ ፣የሚመጣብኝ እንደ አይሁድ በባቡር ታጭቀው ወደ መግደያ ጣቢያ የሚጓጓዙ ዜጎችን ነው፡፡የኤሌክትሪክ ግንባታ ሳይ የሚመጣብኝ የኤሌክትሪክ መግደያ ወንበር ነው፡፡የሚቆፈር ነገር ሳይ ድቅን የሚልብኝ የጅምላ መቃብር ነው፡፡

የዞን ዘጠኝ ጀግኖች ብረሳችሁ ታሪክ ይርሳኝ፡፡ባንድ በኩል የዘመናችሁ ተካፋይ በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል፡፡በሌላ በኩል፣ የመከራችሁ ተካፋይ ባለመሆኔ ሐፍረቱን አልችለውም፡፡ያም ሆኖ‹‹በሉ እናንተም ሂዱ እኛም ወደዛው ነው፡፡ወትሮም መንገደኛ ፊትና ኋላ ነው›› የሚለው የዓለሙ አጋ የበገና እንጉርጉሮ ባጸደ-ነፍስ ላሉት ብቻ ሳይሆን ባጸደ-ወህኒ ላሉትም ይሆናል፡፡ስሜቴን እንዴት መግለጽ እንዳለብኝ አላቅም፡፡የገላውድዮስ ዜና- መዋእል ጸሐፊ በዚህ ሰዓት የሚሰማኝ ስሜት ከምእተ አመታት በፊት ተሰምቶት ነበር፡፡
መዓልትኒ ኮነ ሌሊተ፣ዘኢነአምሮ ወጽልመት ዘኢልማድ መጽአ
ወደፈነ እንስሳ ወሰብአ
(ቀኑ ሌሊት ሆነና፣ ወጋገኑ ተሰደደ
እንግዳ ጨለማ መጣ፣ጠባዩ ያልተለመደ
ሰውን፣ እንስሳን ጋረደ)


(የተማሪዎቹ ግድያ ጉዳይ) ከማስተር ፕላኑ ግጭት ባሻገር

$
0
0

***** (ዜና መዋዕል)27/8/06

የሰሞኑን የአዲስ አበባንና የኦሮሚያ ልዩ ዞን የጋራ ማስተር ፕላን ተከትሎ የተነሳውን ተቃውሞና ግድያ በሚመለከት እንደ አንድ ግፍንና በደልን እንደሚጠላ ዜጋ ጥልቅ ሃዘን ይሰማኛል፡፡ ነገሩ በኛ ሀገር ሆነና ነው እንጅ ስልጣን የሚያስለቅቅና በግድያው የተሳተፉትንም በህግ የሚያስጠይቅ በሆነ ነበር፡፡ በየትኛውም ሁኔታ በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞውን የሚያቀርብ ዜጋ እንኳን ሞት ድብደባም አይገባውም፡፡ ረብሻና ሁከት ፈጣሪዎች እንኳ ሲያጋጥሙ በሰለጠነ መንገድ በቁጥጥር ስር አውሎ ለህግ ማቅረብ ተገቢ ነበር፡፡ ይህ ግን በኛ ሀገር ሊታሰብ የሚችል አይደለም፡፡ ከግጭቱ ባሻገር ግን ሰከን ብለን ልናነሳቸው የሚገቡ ነገሮች አሉ፤ እኔም በዚህ ጽሁፍ የማተኩረው በዚሁ ነው፡፡
tplf killing ethiopians
ከ85% በላይ የሆነው ህዝብ ኋላ ቀር በሆነ የግብርና ዘዴ ህይወቱን በሚመራባት ሀገራችን የከተሜነት ወይም የኢንዱስትሪውና የአገልግሎት ሰጪው ዘርፍ መስፋፋት ጠቀሜታው አሌ የሚባል አይደለም፡፡

በአዲስ አበባ ዙሪያ ያሉ የኦሮሚያ አካባቢዎችም ከአ/አበባ በረከቷንም ሆነ ርግማኗን መካፈላቸው አልቀረም፡፡ በተለይም ከከተማዋ መስፋት ጋር በተያያዘ በዙሪያው ያሉ የኦሮሚያ ገበሬዎች ይዞታቸውን ባልተጠናና ህጋዊ ባልሆነ መንገድ እየሸጡ እርሻቸውን እያጠበቡ፤ ከተሞቹም ለዘላቂ ልማት አመቺ ባልሆነ መንገድ እየተስፋፉና ከአ/አበባ ጋር እየገጠሙ መሆኑን እያየን ነው፡፡ ዞሮ ዞሮ ገበሬው ባለችው ጥሪት የሚያስተምራቸው ልጆቹን አምራችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማቱ ተስፋፍተው ካልቀጠሩለት ስራ አጥ ልጁ ተመልሶ የእሱኑ መሬት እየተቀራመተ ድህነቱን ማባባሱ አይቀርም፡፡
በመሆኑም በማስተር ፕላኑ በዙሪያው ያሉ የኦሮሚያ አካባቢዎች ወደ አ/አበባ ተካለሉም አልተካለሉ ይህንን የከተሜነት ወይም የኢንዱስትሪና አገልግሎቱን ዕድገት ታሳቢ አድርጎ በቅንጅት መስራቱ ለኔ በግሌ ጥቅሙ እንጅ ጉዳቱ አይታየኝም፡፡ ነገር ግን ከቀደመው የመንግስት አፈፃፀም ግድፈቶችና ከአጠቃላይ የስርዓቱ ችግር ስንነሳ የምንቃወምባቸው በቂ ምክንያቶች ይኖራሉ፡፡

ምንም እንኳ የጋራ ማሰተር ፕላኑ ለውይይት በቀረበበት ወቅት የኦሮሚያ ካድሬዎች ያቀረቧቸው ጥያቄዎች በህገ መንግስቱ መሰረት ክልሉ ከአ/አበባ ሊያገኛቸው ስለሚገባው ጥቅሞች ቢሆንም በቀጣይ ባለድርሻ አካላት ይወያዩበታል መባሉ ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጅ፡-
1- ባለድርሻ አካላት ተወያይተው የጋራ ማስተር ፕላኑ ይቅር ቢሉ እንኳ መንግስት ከማድረግ ወደኋላ የማይልና የሚስማሙለትን ብቻ መርጦ የሚያወያይ፣ ውሳኔውንም የሚያስደግፍ መሆኑን ከቀደመው የመንግስት አካሄድ የምንረዳ መሆኑ፤
2- ገበሬዎቹም በልማት ስም ሲነሱ የሚሰጣቸው ካሳ በዘላቂነት ህይወታቸውን ለመምራት የማያስችላቸው መሆኑ፤
3- ስርዓቱ ለገበሬው ዝቅተኛ ካሳ ከፍሎ በከፍተኛ የሊዝ ዋጋ የሚሸጠው መሬት ገንዘቡ ኃላፊነትና ተጠያቂነት በተሞላበት መንገድ ለህዝብና ለሀገር ጥቅም መዋሉን እንድንጠራጠር የሚያደርገን የመንግስት ባለስልጣናት ሃይ ባይ ያጣው ዘረፋና ሙሰኝነት፤
4- እንዲሁም መሬቱን በፍትሃዊነት ሀገርና ህዝብን ለሚጠቅሙ ሳይሆን የስርዓቱን ደጋፊዎችና ተጠቃሚዎች የኢኮኖሚ የበላይነት ለማስቀጠል ሲባል በአሻጥር እነዚሁ ልማታዊ ተብዬ ባለሀብቶች የሚቃረጡት መሆኑ ጥያቄ እንድናነሳ ከበቂ በላይ ምክንያቶች ይሆናሉ፡፡
ጥያቄውን የምናነሳበት መንገድና ዘዴ ግን የምንፈልገውን ምላሽ ለማግኘት ያለንን ዕድል ይወስናል፡፡ ጉዳዩን የአንድ ብሄር ችግር አድርገን የምናነሳው ከሆነ ትልቁ ችግር እዚያ ጋ ይጀምራል፡፡ ሲጀመር በጋምቤላ ነዋሪዎቹ እየተፈናቀሉ ከህንድና ከአረቢያ የመጡ ኢንቨስተር ተብየዎች ከነፃ ባልተሸለ ዋጋ መሬቱን ሲነጥቁት አብረነው ስላልጮህን ዛሬ አብሮን ላይቆም፤ አማራው ህይወቱን መስርቶ ተረጋግቶ ሲኖርበት ከነበረው ቀዬ አማራ በመሆኑ ብቻ ሲፈናቀልና ከክልላችን ውጣ ሲባል የአማራው ችግር ብቻ አድርገን በማየታችን ዛሬ አብሮን ላይቆም ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ገዢዎቻችን (ይቅርታ መሪዎቻችን ወይም አስተዳዳሪዎቻችን አልልም) እስካሁን ሲጠቀሙበት ለነበረው የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲያቸው መጠቀሚያ መሆናችንን ነው፡፡ በተለያየ ጊዜና ሁኔታ ለያይቶ የሚያጠቃን ስርዓት ዋናው ዓላማ ተባብረን እንዳንቆምና መብቶቻችንን እንዳንጠይቅ ነው፡፡
ይህ ደግሞ ተሳክቶላቸዋል፡፡ በሰሞኑ ተቃውሞ እንኳ ብሄር ለይቶ ከመቋሰሉ በተጨማሪ ጥያቄውን ሌላ መልክ ለማላበስ ምንም እንኳ ጥያቄውን ያነሱት ተማሪዎች ዓላማቸው ነበር ብለን ባንገምትም እሱን ታከው በአንዳንድ ቦታዎች ሰዎች ላይ ጉዳት ያደረሱት፣ ንብረት ያወደሙትና የዘረፉት የራሳቸው ግብ እንደነበራቸው መካድ አይቻልም፡፡

ወደ እውነታው ስንመጣ ሱሉልታና ጫንጮ ለሚኖረው ኦሮሞ ባሌና ሐረር ከሚገኘው ኦሮሞ የሰሜን ሸዋ አማራ በባህልም በእምነትም ይቀርበዋል፡፡ አብሮ የኖረውን ሕዝብ አማራ ስላልሆነ ብቻ ሲጠቃ ዝም ይላል ማለት አይደለም፡፡ ኦሮሞውም አማራ ሲጠቃ ዝም አይልማ፡፡ ምናልባት ራሱን የተማረ ብሎ ከሚጠራውና በተግባር ግን ካልተማሩት አባቶቹ ካነሰው እንዲሁም ለርካሽ የፖለቲካ ትርፍና ሕዝብና ሕዝብን በማጋጨት ሆዳቸውን ለመሙላት ከሚያስቡ ደም አፍሳሾች ውጭ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ተቻችሎ ተከባብሮና ተፈቃቅሮ የሚኖር መሆኑን አንዱ ካንዱ ተጋብቶ ወልዶን ስላሳደገንና አብረንውም ስለምንኖር እናውቀዋለን፤ ይህንንም ለመረዳት ነጋሪ አያሻንም፡፡

ስለሆነም የሕዝቡን የመብት ጥያቄ በጠባብ ብሄርተኝነትና ጽንፈኝነት ተመርቶ ከማጥበብ ይልቅ፡-
- የሁሉም ኢትዮጵያውያን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ፣
- በማንኛውም ቦታ ሰዎች ያለአግባብ እንዳይፈናቀሉና አስፈላጊ ከሆነም ፍትሃዊና ተገቢ ካሳ እንዲያገኙ፣
- በስልጣን ላይ ያለው መንግስት የሕዝቡን የስልጠን ባለቤትነት እንዲያከብርና ህገመንግስታዊ መሰረት የሌላቸውን አፋኝ ህጎቹን እንዲያሻሽል፣
- የስርዓቱ ብልሹ አስተዳደር እንዲሻሻል ካልሆነም ስልጣን እንዲለቅና
- ሁሉም ኢትዮጵያዊ በእኩልነትና በነፃነት የሚኖርባት ለሁላችንም የምትመች ሀገር እንድትኖረን ተባብረን በጋራ መቆምና መታገል ይገባል፡፡
ከሁከትና ብጥብጥ እንዲሁም ሌላውን ከማግለልና ከጥላቻ ፖለቲካ ከጥቂት አውቅልሃለሁ ባዮች ውጭ እንደሕዝብ የምንጠቀመው ስለሌለ በተለይ የተማረውና የሚማረው የህብረተሰቡ ክፍል ይህን ነቅቶ ሊከላከለው ይገባል፡፡
አምላክ ኢትዮጵያን ይባርክ!

የገንዘባችን ዋጋ ስንት ነው?

$
0
0

ኤድመን ተስፋዬ *
* (የግብርናና ኢኮኖሚስት እና የገጠር ልማት ባለሞያ)

ethiopia-100birr
የ ፅሁፌ ትኩረት የገንዘባችንን ዋጋ በመፈተሸ ከንድፈ ሀሳብ እና ከሀገራት የኢኮኖሚ ታሪክ መነሻነት መንግስት ለዋጋ ግሽበቱ የሚሰጠውን የኢኮኖሚ እድገት ምክንያትነት ከመሞገት በተጨማሪ ከዋጋ ግሽበቱ ጀርባ አጮልቆ ማየት ነው፡፡ መነሻችን ኑሮአችን ነው ኑሮአችን ስንል ደግሞ ገንዘባችን አንዱ ና ዋነኛው ከመሆኑ አኩአያ እንቆቅልሽ የሆነብንን የገንዘባችን ዋጋ ከመግዛት አቅሙ አንፃር ዋጋውን በመፈተሽ በዋጋ ግሽበት አማካኝነት ገንዘባችንን መሰረቅ አለመሰረቃችንን መፈተሽ የሚያስፈልግ ይመስለኛል፣ የምን መሰረቅ ካሉ ከዛሬ አንድ ወር በፊት ዘንቢል ይዘው ወደ ገበያ ወጡ እንበል በ መቶ ብር ዘንቢሎን በመሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች ሞልተው ተመለሱ እንደገና ከ አንድ ወር ወይም ከ አራት ወር በሁአላ በተመሳሳይ መልኩ ከአንድ ወር በፊት የሸመቱትን እቃ ለመሸመት መቶ ብር ይዘው ሲወጡ መቶ ብሮ ሊገዛሎት የቻለው እቃ ከዘንቢሉ ግማሽ አላለፈም እንበል ምክንያቱ ደግሞ በገንዘቡ የመግዛት አቅም መቀነስ የተነሳ በኪሶ የያዙትን ገንዘብ በመሰረቆኦ ነው:: ይህም ማለት የአንድ ብር ኖት የዋጋ ግሽበቱ 30 ፐርሰንት በሆነበት ሁናቴ ያለው ዋጋ (1 /1.30) 0.76 ወይም ሰባ አምስት ሳንቲም በመሆኑ ሃያ አምስት ሳንቲም ከአንድ ብር ላይ እንደ መሰረቅ ማለት ነው ፡፡ ስለ ገንዘብ የመግዛት አቅም መቀነስ ወይም ስለ ዋጋ ግሽበት ሲነሳ በአሁኑ ወቅት ምሳሌ የምትሆነው የሮበርት ሙጋቤ ሀገር ዙንባቤ ነች፣ የዙንባቤ ገንዘብ ከመውደቁ የተነሳ በዙንባቤ ከተሞች በፌስታል ሙሉ ገንዘብ ቢያዩ ከገንዘቡ ይልቅ ፌስታሉ ዋጋ እንዳለው ማወቅ አለቦት በሚል ደረጃ እስኪቀለድበት ድረስ ገንዘባቸው የማገበያየት አቅሙ ሞታል፡፡ በሀገራችንም በአብዛኛው ህብረተሰብ ምነው ገንዘባችን የሱማሌ (ሱማሌ ከወራሪው ዚያድባሬ መውደቅ ጀምሮ እሰከ አሁን ምን ያህል ገንዘቡአ የማገበያየት አቅሙ እንደሞተ ልብ ይሉአል) ብር ሆነ በሌላ በኩል የኛን መቶ ብር ከ ከጃማይካዊው ዩዝየን ቦልት ጋር በማመሳሰል ዩዝየን ቦልት መቶ ሜትሩን ከ አስር ሰከንድ እንደሚገባው ሁሉ የኛም የመቶ ብር ኖት ተዘርዝሮ ለማለቅ ከአስር ሰከንድ ያላነሰ ጊዜ ነው የሚወስድበት የሚል እና ሌሎች ተመሳሳይ ማህበረሰባዊ ትዝብቶች እና ብሶቶች የገንዘባችንን የመግዛት አቅም መድከምን እና የኑሮ ውድነትን ተንተርሶ ይነሳሉ፡፡ በአንድ ወቅት በፖርላማ የሀገራችንን የዋጋ ግሽበት አደገኛነት በመግለፅ የግሽበቱን ምክንያት ከመንግስት ቅጥ ያጣ የገንዘብ ወጪ ስርአት ጋር የተገኛኘ መሆኑን አፅንኦት በመስጠት እንዲሁም መንግስት የበጀት ጉድለቱን ለመሙላት ተጨማሪ የገንዘብ መጠን ወደ ኢኮኖሚው በማስገባቱ ግሽበቱን እንዳባባሰው በመግለፅ መንግስት ወጪውን እንዲቀንስ በአንድ የተከበሩ የፓርላማ አባል ለተነሳው ጥያቄ ነብሳቸውን ይማርና የቀድሞው የሀገራችን ጠቅላይ ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊ በሰጡት መልስ ከኢኮኖሚ እድገት ጋር ተያይዞ የዋጋ ግሽበት ( inflation) መከሰቱ አዲስ ነገር አለመሆኑን በመግለፅ የዋጋ ግሽበቱ ከኢኮኖሚው እድገቱ ጋር በተመጣጠነ መልኩ የተከሰተ መሆኑን በማብራራት ለዋጋ ግሽበቱ ሲባል የሚቀነስን የመንግስት ወጪ ልማትን ከመቀነስ ጋር አያይዘው ጫማ ጠበበኝ በሚል እግር አይቆረጥም ሲሉ ኬይኔዥአዊ መልስ ሰጥተዋል፡፡ የኬይኒዝ የኢኮኖሚክስ ንድፈ ሀሳብ እንደ ሚያወሳው መሀከለኛ የሆነ የዋጋ ግሽበት የኢኮኖሚ እድገትን በማቀላጠፍ የኢኮኖሚ እድገት አቀጣጣይ መሳሪያ ሊሆን ይችላል ይህ ሊሳካ የሚችለው ግን እንደ ኬይኒዝ የኢኮኖሚክስ ንድፈ ሀሳብ መሰረት መሀከለኛ (moderate) የሆነው የዋጋ ግሽበቱ የመቆጠብ አቅማቸው አናሳ ከሆኑት የሰራተኛው እና የአርሶ አደሩ መደብ ሀብትን ወደ ካፒታሊስቱ በማሸጋገር የመዋእለ ነዋይ ፍሰትን በማስፋፈት እና በማቀላጠፍ ለኢኮኖሚ እድገት አዎንታዊ ሚና መጫወት ሲችል ነው ይህንን ለማሳካት ደግሞ የኢኮኖሚ ስርአቱ በፍላጎት እና በአቅርቦት መርህ መመራት ይኖርበታል ፡፡ በኢኮኖሚ ውስጥ ሙሉ የስራ እድል ወይም ሙሉ ሰራተኛ መኖርን እንደ ቅድመ ሀሳብ (Assuption) እንደመነሻ በመውሰድ የዋጋ ግሽበትን እና የኢኮኖሚ እድገትን ዝምድና የሚተነትነውን የሞላ የስራ እድል (full employment model) የሚባለውን የኢኮኖሚክስ ሞዴል መነሻ ብናደርግ የስራ እድል ወይም ሰራተኛ ሙሉ በሆነበት የኢኮኖሚ ስርአት የኢኮኖሚ እድገት ከኢኮኖሚ እድገቱ ስፋት አኩአያ ላልተጠበቀ የዋጋ ግሽበት ምክንያት ሊሆን ይችላል ነገር ግን የድህነት ስፋቱ በገዘፈበት ሀገር ከ 10-12 % የኢኮኖሚ እድገት በተመዘገበበት ሁናቴ 35-40 % የዋጋ ግሽበት ተከስቶ ከኢኮኖሚ እድገቱ ጋር ማያያዝ የተጋነነ ሲሆን እንዲያውም በእንደዚህ አይነት የኢኮኖሚ እድገት መጠን ይህ አይነቱ የዋጋ ግሽበት የኢኮኖሚውን ጤናማ አለመሆን አመላካች ነው፡፡

የዋጋ ግሽበት ምክንያቶች ስንል

በኢኮኖሚ ስርአት ውስጥ ከልኬቱ ያለፈ የዋጋ ግሽበት ወይም የገንዘብ የመግዛት አቅም መውደቅ( inflation) በሀገር ላይ ከኢኮኖሚያዊ መመሰቃቀል ባለፈ ለማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መመሰቃቀል ምክንያት ሊሆን ይችላል፣ የገንዘብ ኢኮኖሚስቶች የዋጋ ግሽበትን ወይም የገንዘብ የመግዛት አቅም መውደቅን (inflation) በዜጎች ላይ የሚፈጸም ስርቆት በማለት ይገልፁታል፡፡ የዋጋ ግሽበት ወይም የገንዘብ የመግዛት አቅም መውደቅን የሚያስከትሉ መንስኤዎች ፍላጎታዊ ( demand pull) እና ወጪያዊ ግፊቶች (cost push) ሲሆኑ በወጪያዊ ግፊቶች ምክንያት የሚባለው የሰራተኛ ዋጋ መናር፣ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ፣ የግብርና ግብአቶች መወደድ ፣ በምንዛሬ መወደድ የተነሳ ከውጪ የሚገቡ ግብአቶች መወደድ፣ በሀይል ዕጥረት የተነሳ የምርታማነት ግብአቶችን መወደድን ተከትሎ አምራቹ አካል ኪሳራን በመፍራት በሚጨምረው የእቃዎች ዋጋ ምክንያት የሚከሰት የዋጋ ግሽበት ሲሆን ፍላጎታዊ ምክንያት የሚባለው ደግሞ ከገቢ መጨመር ጋር የተያያዘ የፍላጎት መጨመር እንዲሁም የአቅርቦት ማነስ ( ሸማቾች አንድአይነት እቃዎችን በተለይ የፍጆታ እቃዎችን የመግዛት ፍላጎት ከአቅርቦት ማነስ ጋር ተያይዞ የሚፈጥረው የዋጋ ንረት)፣ ከመንግስት የበጀት ጉድለት ጋር ተያይዞ የገንዘብ ኖት አቅርቦት መጨመር ጋር ተያይዞ የሚከሰት የዋጋ ግሽበት ነው፡፡ የገንዘብ የመግዛት አቅም መውደቅ( inflation) እስከ 2 % ብቻ ከሆነ በኢኮኖሚው ላይ ይሄነው የሚባል ችግር ሊፈጥር ስለማይችል ጤናማ ለባል ይችላል ከ 2 % በላይ ከሆነ ግን እንደየደረጃው በኢኮኖሚው ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ሲኖረው በተለይ ሀይፐር ( hypher) የሚባለው ደረጃ ከተደረሰ የመገበያያውን ገንዘብ እስከ መለወጥ እንደሚያስደርስ አብዛኛዎቹ የገንዘብ ኢኮኖሚስቶች ይገልፃሉ፡፡

የአንድ ብር የገንዘብ ኖትን ለማተም ወጪው 0.25 ሳንቲም ከሆነ 0.75 (ሰባ አምስት ሳንቲም )ሳንቲሙን ትርፍ የሚያገኘው አንድ ብር አሳታሚው አካል እንደሆነ ለማወቅ የተጋነነ የኢኮኖሚክስ ባለሙያ መሆን አስፈልግም፣ ይህ አይነቱ ንድፈ ሀሳባዊ ምሳሌ መንግስታት የበጀት ጉድለታቸውን ለመሸፈን ከኢኮኖሚው አቅም በላይ ተጨማሪ የገንዘብ ኖትን ብሄራዊ ባንክን በመጠቀም ማተም እንደ አማራጭ የሚወስዱበትን ምክንያት በትንሹ ለመረዳት ያስችለናል፡፡የሀገራት የኢኮኖሚ ታሪክ እንደሚነግረን ደካማ እና በሙሰኛ አመራሮች የተሞላ የመንግስት ስርአት ወጪውን እና የበጀት ጉድለቱን ለመሸፈን እና ለበጀቱ ምንጭነት መበደርን እና የብድርን ምንጭ ከልኬቱ ባለፈ (ከገቢው በላይ) መልኩ ያለ ቅድመ ሁኔታ መጠቀም ሲሆን በዚህም የተነሳ ከመንግስት ስርአቱ ገለልተኛ በመሆን የኢኮኖሚውን የገንዘብ ፍሰት መቆጣጠር እና ማስተካከል የሚገባውን ብሄራዊ ባንክ በፍፁም ገለልተኛ እንዲሆን አይፈቅዱም፡፡ የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋአም በተደጋጋሚ ሁኔታ እንደሚገልፀው በሀገራችን ካለፉት ስምንት እና ዘጠኝ አመታት ወዲህ በኢኮኖሚው ውስጥ የገንዘብ አቅርቦት በተለየ ሁነታ መጨመሩን ሲሆን በባንኮች ያለው የተትረፈረፈ የገንዘብ ክምችት ደግሞ በካሽ ያለውን ብዛት ያለው የገንዘብ ኖት በኢኮኖሚው ውስጥ መኖሩን ማሳያ እንደሆነ ይገልፃል፡፡ እውቁ ኢኮኖሚስት ፍሪድማን አገላለፅ የዋጋ ግሽበት በከፈተኛ መጠን ቀጣይነት ባለው መልኩ ከተከሰተ የገንዘብ አቅርቦቱም በኢኮኖሚ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል፡፡ ዶ/ር አሳየሀኝ ደስታ Economic Growth for Inflation: The Ethiopian Dilemma በተባለው ጥናታዊ ፅሁፋቸው ሀገራችን በዋጋ ግሽበት አዙሪት ውስጥ ለመገኘቱአ በዋናነት የሚያነሱት ምክንያት የገንዘብ ኖት አቅርቦቱን መጨመር ሲሆን ለዚህም ማሳያነት እ.ኤ.አ በ 2002 19.4 % የነበረው የገንዘብ አቅርቦት በ 2006 ወደ 23.3 % መጨመሩን ሲሆን ይህ ሁናቴ ደግሞ ከ 2002- 6 በአማካይ የተመዘገበውን 6.8 % የኢኮኖሚ እድገት ጋር (የኢኮኖሚ እድገቱ በራሱ ግሽበታዊ በሆኑ ምክንያቶች የተሞላ መሆኑ እና በክፍለ ኢኮኖሚዎች ትስስር ላይ የተመሰረተ አለመሆኑ እንዳለ ሆኖ) የገንዘብ ክምችቱን ለማስተካከል የገንዘብ አቅርቦቱን በ 18 % መጨመር ያስፈለገ ሲሆን ይህ ሁናቴ ደግሞ ባለው የዋጋ ግሽበት ላይ በአማካይ ለተጨማሪ የ 12 % የዋጋ ግሽበት ምክንያት መሆኑን በመጥቀስ በዚህ ሁናቴ ውስጥ የመንግስት የበጀት ጉድለት ኔጋቲቭ መሆኑን በመጥቀስ ምንም እንኩአን የገንዘብ አቅርቦቱ መጨመር ለመዋእለ ነዋይ ፍሰቱ ምክንያት ቢሆንም እንኩአን የዋጋ ንረቱን ለመቆጣጠር የመንግስትን የበጀት ጉድለት ማእከል ካልተደገ ዋጋ ቢስ መሆኑን ይጠቅሳሉ፡፡

በሀገራችን የምግብ ፍጆታዎች የሆኑት የግብርና ምርቶች እጥረት ለምግብ ፍጆታዎች ዋጋ ንረተ በምክንያትነት በሚበቀርብበት ወቅት መንግስት የሚሰጠው ምላሽ የምግብ ፍጆታ የሆኑት ምርቶች ዋጋ ሊንር የቻለው በኢኮኖሚ እድገቱ የተነሳ እና አምራቹ ገበሬ ለምርቱ ትክክለኛ ዋጋ በመፈለጉ እንደሆነ ነው ይህም ማለት የግብርና ስራው ህይወቱን ስለ አሻሻለለት ለእለት ፍጆታው ሲል ብቻ ምርቱን ያለ ዋጋው ስለማይሸጥ እንደ ማለት ነው ነገር ግን የአለም አቀፉ የተባበሩት መንግስታት የህፃናት ድርጅት (UNICEF) ሆነ የተባበሩት መንግስታት በሀገራችን በየአመቱ ለምግብ እጥረት የሚጋለጡት ሰዎች ህፃናትን ጨምሮ 26 ሚሊዮን እንደሚደርስ በሚገልፁበት ሁናቴ መጋቢያችን የሆነው አርሶ አደር በግብርናው እንቅስቃሴ የተነሳ ህይወቱ መለወጡን እና ሀብታም መሆኑ ሲገለፅ ጥያቄ ማስነሳቱ አይቀርም፡፡

ያለአግባብ የኬሚካል ግብአቶችን ለ ግብርና በመጠቀም የተነሳ ሀገራችን ከአፍሪካ ከፈተኛ የፀረ ተባይ (pesticides) መድሀኒት ክምችት የሚገኝባት ቀዳሚ ሀገር መሆንዋን ኤድዋርድ የተባሉ አጥኚ Greening Ethiopia for self-sufficiency. በተባለው ጥናታዊ ጽሁፋቸው ይገልፃሉ፣ በከፍተኛ ደረጃ የኬሚካል ማዳበሪያ መጠቀምን ተከትሎ የገጠሩ አምራች የሆነው የግብርና መሬት ለስነምህዳራዊ ችግር የተጋለጠ ሲሆን የችግር መጠኑም ከ መሬት ምርታማነት መውደቅ እስከ የአየር ንብረት ለውጥ ምክንያትነት የሚደርስ ሲሆን ይህም በዝናብ ላይ ጥገኛ የሆነውን የግብርና ክፍለ ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ ሲሆን ይህም የሚያሳየን የግብርና ምርቶች ዋጋ መናር መንስኤን ውስን የሆነ የግብርና ምርታማነት ቴክኖሎጂ በገጠሩ አካባቢ በመኖሩ የተነሳ የሚለው የሚገልፀው ይመስለኛል ፡፡

ከዋጋ ግሽበት ጀርባ

ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት ቀጣይነት ባለው መልኩ በሚከሰትበት ሁናቴ በኢኮኖሚው ስርአት ውስጥ የሚተገበር የወለድ ተመን ፖሊሲ የዋጋ ግሽበትን መጠን ማእከል በማድረግ የኢኮኖሚ ስርአቱን ሚዛናዊነት በጠበቀ መልኩ እና የዋጋ ግሽበቱን ከመቀነስ አኩአያ በተመቻመቸ መልኩ ተግባራዊ ካልሆነ በባንኮች ና በፋይናንስ ተቋአማት ውስጥ የሚሰጠውን የቁጠባ ና የብድር አገልግሎት በተበዳሪ ሰራቂነት እና በቆጣቢ (በአበዳሪ) ተሰራቂነት መሀል የወደቀ አገልግሎት ያደርገዋል በመሆኑም ትልቁ ጉዳይ ከዋጋ ግሽበት ጋር ተያይዞ የሚፈጠረው የቆጣቢ በ ተበዳሪ መሰረቅ ነው፡፡ የቅርቡን የብሎንበርግ 29.6 % በአማካይ የሚለውን የሀገራችንን ያለፉትን አምስት አመታት የዋጋ ግሽበት መነሻ ብናደርግ ከወለድ ተመኑ (አማካይ ከ 8-10%) ጋር ባነፃፀረ መልኩ የዋጋ ግሽበቱን ያማከለው የወለድ ተመን ኔጋቲቭ 20 % መሆኑን እንረዳለን ይህ ማለት ደግሞ አንድ ተበዳሪ ( ከባንክ ተበዳሪ የሆነ ግለሰብ) ከአበዳሪ (ብሩን በባንክ ውስጥ ቆጣቢ ከሆነ ግለሰብ) 100 ብር ቢበደር አበዳሪው ተጨማሪ 20 ብር ገንዘቡን እንዲጠቀም ለተበዳሪው መክፈል እንደማለት ነው ይህን ወደ ጠቅላላው የኢኮኖሚ ስርአት ስንመልሰው በዋጋ ግሽበት አማካኝነት ባንክ ውስጥ ቆጣቢ ከሆነው ግለሰብ ወደ ባንክ ተበዳሪው ግለሰብ የሚሸጋገርን ሀብት መነሻ በማድረግ በዋጋ ግሽበት አማካኝነት በጠቅላላው ኢኮኖሚ ውስጥ የሚፈጠርን የሀብት ሽግግር ለመገንዘብ አዳጋች አይሆንም በተጨማሪም በዋጋ ግሽበት ወቅት በቢሮክራሳዊ እና በጥቅመኝነት የተነሳ የተወሰኑ አካላትን እና ድርጅቶችን ብቻ ያማከለ ከፍተኛ መጠን ባለው የብር መጠን ደረጃ የብድር አገልግሎት መኖሩ ሰራቂን ማዘጋጀት እንዳለ ለመገንዘብ አዳጋች አይደለም፣ የትኛው ኢኮኖሚስት ነበር ለሰላምታ እንኩአን ለፖለቲከኞች እጆቼን ከዘረጋውላቸው እና ሰላምታ ከተለዋወጥን በሁአላ ጣቶቼን እቆጥራቸዋለው ምክንያቱም ሊሰረቁ ይችላሉና በማለት የተናገረው፡፡

በሬየን አልሸጥም –አጭር ወግ –በሄኖክ የሺጥላ*

$
0
0

Henok Yeshitila

አዲሱን (የነበረውን ግን ሰሞኑን የሾረውን) የ “ኦሮሞ ወጣቶች ” ግድያ። በነገራችን ላይ ለምንድን ነው “የኢትዮጵያ ወጣቶች ” የማንለው? ማለት ስለማንፈልግ? ወይስ ብንል ባንል ምን ይጠቅማል ( ምንስ ይጎዳል በሚል ሃሳብ?) ሁለቱንም ያዙልንና እንቀጥል።

ሰሞኑን አምቦ ላይ የተፈጸመውን ግድያ  ተከትሎ ወዳጆች ” ልጅ ሄኖክ በዚህ ጉዳይ ላይ አንድ ነገር በል እንጂ “ጠላቶች ደሞ ” አንተ ምንትስ አማራ አሁን አማራ ቢሆን ኖሮ ይሄ ሁሉ መከራ የደረሰበት አምሳ ገጽ ጽፈህ ፣ ነገሩን ለውጠሕና ለጥጠህ ባቀረብከው ነበር ” የሚሉ መልዕክቶችን አስቀምጠውልኛል። እኔም እንደ ለገዳዲ ሬዲዮ ” ጦማሪዎችች ሆይ ምልእክታችሁ  ደርሶኛል ለሁሉም እንደነገሩ ለመመለስ እንሆ–”

በነገራችን ላይ አማራ ስለመሆኔ እኔ በበኩሌ እርግጠኛ አይደለሁም ፣ ቢያንስ እርግጠኛ እስክሆን ብትታገሱኝ ምን ነበረበት ( ስለ-ኔ ከኔ በተሻለ መልኩ የምታውቀው እናቴ እንኩዋ እንዲህ በሙሉ አፍዋ “አንተ አማራ!”  ብላኝ  አታውቅም። ታዲያ የምታውቀው ነገር ቢኖራትም አይደል ? አለበለዚያ ማኛና ሰርገኛ በሚል ማህበረስብ ውስጥ አድጋ እኔን በደም ስሜ መጥራት ባልዳገታት ” እስኪ ለናቴ ጊዜ እንደሰጠሁዋት እናንተም ለኔ ጊዜ ስጡኝ ” ደሞ ለዘር ፣ እድሜ ለወያኔ እንኩዋን የሰው  የንብ ሰፈር እንኩዋ በታወቀበት ዘመን የምን መንገብገብ ነው!) ።  አቦ እናት ለዘላለም ትኑር ! ቀጣዩን ሃሳብ በሚቀጥለው መስመር ላይ ያንብቡት።

መልስ አንድ:  ለሞቱት ስንገጥም

 

ሲረግጡን ታግሰን

ሲሰድቡን ታግሰን

ይሄን ሁሉ ዘመን ብሶት ተንተርሰን

ሃዘን አኮራምቶን

መላ ቅጡ ጠፍቶን

ሁሉም ግራ ሆኖ

በሃሳብ ተውጠን

ከሥጋ ስማችን

ያፈሩ ከበደን ።

 

እና አይሆንም አልን

ሕጉ ይስተካከል

ይሞረድ ይቦረሽ ባለ ጥርሱ መድብል

ድንበሬን መልሱ ክብሬን እንዳሻችሁ

ነጻነቴን ቀሙኝ ስሜን እባካችሁ።

 

አልጻፍ አልናገር

አልሰለፍ ይቅር

ባልበላም ግድ የለም ዘመን ጾሜን ባድር

አይከፋኝም ከቶ ብሰደድ በገፋ

ሃገሬ ቢቆረጥ ታሪኬ ቢጠፋ

 

አይሞቅ አይበርደንም እኛ ግድ የለንም

ሰው ቢፈናቀል ቢራቆት ቢራብም

 

ወደብ አልባ ብሆን ወይም ወኔ አልባ

እሱ አይደልም ለኔ ከቁብ የሚገባ

 

እያልኩ ልቀጥል አሰብኩና ተውኩት።  እውነት እውነት እላችሁዋለሁ ሰው እንዳይከፋው እያሰቡ ለመጻፍ ከማሰብ የበለጠ  የሚከብድ ነገር ዕኔ በበኩሌ አላጋጠመኝም። ስለ መፈናቀል ጽፈ ሳልጨርስ ስለ አፈናቃዮች መጻፍ በጣም ይከብዳል፣ ስለ ዘረኛ ስርዓት ጽፈ ሳልጨርስ ስለ ዘረኛ ተጨቁዋኝ መጻፍ አሁንም ይከብዳል። ስለ ኢትዮጵያ ተናግሬ ሳልጨርስ ስለ መንዝ ወይም ስለ ኦሮሚያ መጻፍ ይደብታል። ስለ ትግሬ አምባገነን ተናግሬ ሳልጨርስ ስለ አማራ ወይም እሮሞ ታዳጊ አምባገነን ወግኖ መናገር ይከብዳል ።  የነገሩን ውስብስብነት ተረዱልኝ። በደላቸው፣  ስቃያቸው፣ መታሰር መገደላቸው፣ ሁሉም እውነትነት አለው። ግን   ሀሳባቸው ከደረሰባቸው በደል ያንሳል ፣ ስሜታቸው ካሳለፉት መከራ አንጻር ኢምንት ( ታልኢት) ነው፣ ጉልበታቸውን የማያውቁ በትንሽ ነገር የተጠመዱ ታጋዮች ሆኑብኝ፣ ወንድሞቻቸውን የሰዉለትና የምሰዉለት አላማ ከማንነታቸው ይደቃል፣ ጉዋዶች የተሻል ጥያቄ አለ ( ፍንጭ ልስጣችሁ አይደልም ኦሮሚያ  ኢትዮጵያ የኔ ነች የሚል )።   እስኪ አንድ ወደ ሁዋላ እንመለስና እናስብ። ስናስብ ደሞ በርጋታ እናስብ።

አንድ ወደ ሁ-ዋላ

በደርግ ጊዜ የኢትዮጵያ ክፍላተ ሃገራት እንዴት ይካለሉ እንደነበር እናስብ ( ስለ ደርግ ጠቅላይ ግዛት አሰያየም  ብዙ ማውራት አልፈልግም፣ ማወቅ የፈለገ ያንብብ )  ፣ ከዚያ ” የዘመናት ብሶት የወረሰው ጀግናው የ ትግራይ ሰራዊት ( ስሙን ቀይሮ የ ኢህአዲግ የተባለው ) አዲስ አበባ ገባና ዔርትራን ለማስገንጠል የሚመች ሕግ አወጣ፣  በዚህም ሕጉ ኤርትራን  ብ ቻ ሳትሆን የልጅነት ( የእቃቃ ፍቅረኛዬም ) ከነ ኮካ ኮላ ኮርክያችን ( ጥሪታችን) ጋ አብራ ተገነጠለች (የሚገርመው ኮርኪ ሰለሆነ ነው መሰለኝ ይዘሽ መወጣት አትችይም አልተባለችም )። በመቀጠልም 70 ምናምን  ሺ  ሰው የጨረሰውና ያስጨረሰውን   ጦርነት አካሄአዱ ( በቴዲ አፍሮ ቁዋንቁዋ ” ሁለቱ ዝሆኖች”) በኔ ቁዋንቁዋ ዘ-ለቱ  እባብስ።

ያ ጦርነት አንቀጽ ሰላሳ ዘጠኝ ለሰራው ሥራ የማህተም ማድረቂያ ካሳ ነበር።  ከዛ የመሃል ሀገር ሰው ጨዋተው የተጀመረ መስሎት በደስታ ፓርላማ ውስጥ ጨፈረ ( አንዳንዱ ኮፍያውና ሽርጡ እስከሚወልቅ ድረስ ) እና በየቤቱ የዘሩን ቆዳ የስል ጀመር። ጀግናው የኢህአዲግ ሰራዊት ግን ልጅነት ደጎሰ ጨዋታ ፈረሰ አለ ። ድሮስ እግዚአብሔር ሰጠ እግዚሀብሄር ነሳ እንዳለው እዮብ ወያኔ ሰጠ ወያኔ ነሳ ሆነ  ( ስለዚህም ይህ የዘመን ብሶተኛ  ለኤርትራ በደም ለተቀረው ሕዝብ ደሞ በቾክ  ያሰመረውን ሕግ መርገጥ ጀመረ ) እና ከተሜ እንዴት ተደርጎ አለ። እኛ ስንት ነገር ስናስብ የምን ዘሎ መቀላቀል አይነት ነገርም አንዳንዶች ሲናገሩ ሰማናቸው። አንዳንዶቹ ልጆቻቸው በበሽታና በድንቁርና ከማለቃቸው የበለጠ የልጆቻቸው አማርኛ መማር አሳሰባቸው፣ በ 2006  መሬታቸውን ከቀማቸው ይልቅ ከመቶ ዓመት በፊት ቸፍጭፎናል የሚሉትን ሚኒልክን  መውቀስ ቀለላችው፣ የብሔር ብሔረሰቦች መብት እስከመገንጠል በሚለው ይጠደሰጡት ፣ የአንድን ግለሰብ ሃሳቡን በነጻነት የመግለጽ መብቱን ተቃወሙ እና በታንክ እና በ መትረይስ ከሚደበድባቸው ወያኔ ይበልጥ የቴዲ አፍሮ ዘፈን አመማቸው እና በጠራራ ጸሓይ እየተገደሉ  ወያኔ ይሙት ይላሉ ስል ” ቴዲ አፍሮ ይታሰርልን አሉ” ፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ ። ለዚያ ነው እየከፈሉት ያለው መስዋትነት ከያዙት ሃሳብ ይበልጣል ያልኩት ።  ነብሳቸውን አይማረውና የጎሳ ማይክሮ ባይሎጅስቱ ( መለስ )  ይህንን  ቆመው ቢያዩ ምን ይሉ ይሆን ? እንደኔ እንደኔ ” አዋ ይሄኛው ባክቴሪያ ልክ እንደታሰበው ነው ሪ- አክት እያደረገ ያለው፣ ያኛው አሁንም ቢሆን ትንሽ ራይቦሶማል ትራይባል ሴንስ ኢንሰርት ሊደረግበት ያስፈልገዋል ” የሚሉ አይመስላችሁም? አይ እሳቸው ! አይ እኛ !

አንድ ወደ-ፊት 

የትግል ስያሜ ያላማ ግብር ይሆናል ማለት ዘበት ነው። ለምሳሌ ( የትግራይ ነጻ አውጪን እንመልከት)። በመጀመሪያ ትግራይ ማለት ከየት እስከየት ነው ? የመሃል ሃገሩን ትግራይ ይጨምር ነበር ? እንደዚያ ከሆነ የትግራይ ሕዝብ ሳይሆን የትግራይ ኑዋሪዎች ነጻ አውጪ ነበር መባል የነበረበት። ምክናይቱም ትግሬ ትግራይ ውስጥ ብቻ አይደልምና  የሚኖረው። ለምሳሌ የኛ ጎረቤት የነበሩት እማማ ሐዳስ ( እድሜ ለ ወያኔ የተንጣለለ ቤት ሰርተው ወደ ሳር ቤት ገቡ እንጂ ትግሬ ነበሩ። ግን ነጻ ስለመውጣታቸው እርግጠኛ አይደለሁም።

አሁንም ወደ ነገሬ ልመለስ ( ማንሽ አንቺ በዛሁ የጠፋሁ እንደሁ መልሽን )። ይሄ በተያያዘ ሃሳብ የመጥፋት ችግር አለብኝ ”

አሁንም የስያሜ ጦርነትን የሚቀድም ነገር ያለ ይመስለኛል ( እንዲሁ ሳስበው ፣ አያርገውና የኦሮሞ ሕዝብ ምናምን የሚባል ድርጅት አዲስ አበባን ” ፍንፍኔን በሸዋኛ ” ወይም ” ፊንፍኔ በኦሮምኛ” እዚህ ጋ ቶሎሳ እና ተሎሳ ብለው ሲጣሉ ስላየሁ ጥንቃቄ ቀድሜ ባረግ ብዬ ነው፣ ለማስመልስ ባደረጉት ጥረት ወያኔን ሳያስቡት ገለበጡት እንበል ( ልክ ወያኔ ሳያስበው አዲስ አበባ እንደደረሰ ) ከዛ ምን የሚሆን ይመስላችሁዋል ? እናንተ ለመመለስ ትፈሩ ይሆናል ሌኔ ግን የሞተው መለስ  በኦሮሞ ልጆች ስም; በኦሮሞ ልጆች ደም ፣ በኦሮሞ ልጆች አፈር ብቅ የሚል ይመስለኛል። ከስያሜ ማንነት ይቀድማል። ማንነታችንን ሳናስከብር ስለ ምንነታችን መናገር አንችልም ( ” መ ስፍን ወ/ማርያም እንዳሉት)።  መቼ ነው የነሱን ጨዋታ መጫወት የምናቆመው ? መቼ ?

 

ወግ

አንድ ገበሬ እጅግ የሚወደው በሬውን ሊሸጥ ገበያ ይዞ ይወጣና ሳይሸጥ  ይዞ ይመለሳል።

ዘመድ “ምነው ጃል በሬህን የሚገዛ ሰው አጣህ?”

ገበሬ ” አይ በሬዬን  ሊገዙ ከመጡት ሰዎች መሃል አንዳቸውም  ለበሬው የሚሆን ድርቆሽ ( መኖ ወይም ሳር ) አልነበራቸውም፣ ስለዚህ በሬየን ሽጬ በረሀብ ከምገልው ብዬ ነው ሳልሽጥ  ይዤው የተመለስኩ ”

እኔም እንዲህ ነው የሚታየኝ።  ወያኔ መውደቅ ስላለበት ተብሎ በሬዬን በርሃብ ለሚገል ገበያተኛ ነጻነቴን አልሸጥም። እንሱም (ወያኔዎችም) ቢሆን  ሲጠነሰሱ እርሾዋቸው ዘረኝነት ነበረና። በሬዬን ልተገዛ ከፈለክ መጀመሪያ ሳር ይኑርህ ፣ መጀመሪያ የሚገዛ ሃሳብ ይኑርህ፣ መጀመሪያ ስለ በሬ እወቅ።  አስራ ስምንት ሚሊዮን ጭቁን፣  አስራ ስድስት ሚሊዮን ጭቁን ቢጠላ ጥላቻው  ወተት አይወጣውም እሱንም የሚጠላውንም  ይዞ ይጠፋል እንጂ።  ብሬ መግዛቱ አይደልም ቁም ነገሩ ፣ ቁም ነገሩ እስክታርደው ድረስም በሬነቱን መገንዘብ ነው።

ገበያ ወጥቶ ሸማች መሆን አይደለም ቁም ነገሩ፣ ቀም ነገሩ ቢያንስ የሸማች ባህሪ ይዞ መገኘት ነው።

በአንድነት ለመቆም አንድ አይነት አመለካከት የግድ ሊኖር ይገባል በሚለው ሃሳብ ብስማማም በይበልጥ የሚያስማማኝ አንድ አይነት አላማ ሊኖር ይገባል የሚለው ነው።

እስከሚገባኝ የታጋይ ሃሳብ የጨቆኑትን ከማሸነፍ፣ የገደሉትን ከማንበርከክ፣ የበደሉትን ከመበደልም የራቀና የላቀ መሆን አለበት ብዬ አስባለው። በታጋይና በበቀልተኛ መሃከል ያለው ልዩነት ይሄም ይመስለኛል። ታጋይ አንድን ስርዓት ሲቃወም ወይም ሲታገል፣ ስርዓቱ ማድረግ የነበረበት ግን ያላደረገውን ነገር ለመለወጥ ይመስለኛል፣ አንድ ታጋይ አንድን ስርዓት ለመለወጥ ሲነሳ ፣ ኢ-ፍትሃውነትንም ሆነ የአስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት እውቀቱና ብቃቱ እንዳለው አምኖ ያ እውቀቱና ብቃቱ ስልጣን ላይ ባለው ስራዓት ( ስርዓቱ በሚፈቅደው መንገድ ታግሎ ) እውቅናን ሲነፈግ ፣ ያ የሚያልመውን ለውጥ ለማምጣት እምቢ ያለ አካል ነው ብዬም አስባለሁ። በቀልተኛ ግን የድሮ ቁስሉንና ብሶቱን ከማሰብ እና ብድሩን እንዴት እንደሚመልስ ከማውተንተን ያለፈ ሕልም የለውም፣ ለሱ የሥርዓት ለውጥ ማለት የበደሉትን ( ወይም በድለውኛል በሎ የሚያምነውን) ማህበረሰብ መበደል ነው፣ ለሱ ትግል ቂሙን የሚወጣበት ፣ እልሁንና ቁጭቱን የሚገልጽበት አጋጣሚ መፈለግ ነው። ወያኔ የተፈጠረው በዚህ መንገድ ነው፣ ሌላውም በዚህ መንገድ መሄድ ይፈልጋል ፣ እንደ ዜጋ የተሻለ ሃሳብ ከሌለህ፣ ከቂመኛነት ወደ ታጋይነት፣ ከባለ አረርንት ወደ ባለ ር-አይነት መለወጥ ካልቻልክ በሬየን አልሸጥም።

ቸር ይግጠመን

 

 

 

* ገጣሚው

 

ልክ የዛሬ 17 ዓመት ሚያዝያ 30 ቀን 1989 ዓ.ም አቶ አሰፋ ማሩ ወደ ቤቱ ሊገባ ሲል በወያኔ ተረሽኖ ሕይወቱ አለፈ

$
0
0

ethiopian teachers
በስደት ከሚገኙ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት የተሰጠ መግለጫ

የኢመማ ጀግኖች ሰማእታትን እናስብ።

የዛሬ 17 ዓመት ሚያዚያ 30 ቀን 1989 ዓ.ም አቶ አስፋ ማሩ ከቤቱ በሰላም ወጥቶ ወደ ሥራ በመሔድ ላይ እያለ በአዲስ አበባ ሐምሌ19 የሕዝብ መነፈሸ አካባቢ በጠራራ ጸሐይ በወያኔ/ኢህአዴግ ነፍሰ ገዳይ ፖሊሶች የጥይት እሩምታ ሰለባ የሆነ ጀግና ኢትዮጵያዊ ነው።
Asefa Maru

አቶ አሰፋ ማሩ በጊዜው በወሎ ክፍለሀገር በላስታ አውራጃ መቄት ወረዳ በ1951ዓ.ም ተወለደ። በመምህርነት ሙያ ከማገልገሉም ባሻገር በሙያ ማህበሩ የአመራር አባል በመሆንም የመምህራንን መብትና ጥቅም ለማስከበር ፣ የትምህርቱን ጥራት ለማስጠበቅ በሚደረገው ትግል በግምባር ቀደምትነት ከሚታገሉት አንዱ ሆኖ ሕይወቱ በግፈኞች እስካለፈበት ዕለት በጽናት ቆሞ ቆይቷል። በወቅቱ በነበረው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤም በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት የላቀ ድርሻ አበርክቷል።

በዚህ በኩል ኢመማ ለሙያው ክብር ፣ለትምህርት ጥራትና በእኩልነት መዳረስ፣ በነፃ ለመደራጃት፣ ለሰብአዊ መብቶች መጠበቅ ፣ ለፍትሕና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መስፈን በአጠቃላይ ለአገር ሁለንተናዊ ዕድገት ታግለው እያታገሉ መሰዋዕትነት የከፈሉ በርካታ ጀግኖችን አፍርቷል። አቶ ሺመልስ ዘውዴ በወያኔ/ኢህአዴግ ፖሊስ ጣቢያ ለአንድ ወር ያህል ታስሮ በነበረበት ጊዜ ለከፋ ብርድ ሕመም በመጋለጡ፣ ሕክምና ባለመግኘቱና በደረሰበት እንግልት ከእስር ከተፈታ በኋላ ወዲያውኑ ሕይወቱ አልፏል። አቶ ከበደ ደስታ በኢመማ ሥር የአባት መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት የነበሩትም ታሰረው ሕይወታቸው እስር ቤት እንዳሉ አልፏል። እቶ አወቀ ሙሉጌታ የኢመማ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና በጥንካሬው የምናደንቀው የኢመማን ጽ/ቤት ለተላጣፊ ለአለመስጠት የሙጥኝ እንዳለ አሟሟቱ በግልፅ ሳይታወቅ በመጋቢት ወር 1999ዓ.ም መንገድ ላይ ሞቶ ተገኝቷል። አቶ ሰርዶ ቶላ፣አቶ
ፈቃዱ ፍርዴና ሌሎችም ኢመማ ካፈራቸውና በዕምነነታቸው ጸንተው ካለፉት ጀግኖች ቀዳሚዎች ናቸው። በቅርቡ በሕዳር ወር 2004ዓ.ም ደግሞ ፍትሕ በሌለበት አገር መኖር ባዶ ሕይወት ነው በማለት ራሱን በጋዝ አንድዶ መስዋዕት የሆነው መምህር የኔ ሰው ገብሬ ቆራጥነቱ ሕዝቡን ያስደመመ ሆኖ አልፏል።መምህራን በተለይ ማህበረሰቡ በአጠቃላይ ለእነዚህ ለኢመማ ጀግኖች ክብርና ሞገስ እንደሚያጎናጽፏቸው እናምናለን። የተሰውለትን ቅዱስ ዓላማ ከግቡ ለማድረስ ከሁላችንም አገራዊና ሕዝባዊ ግዴታ ይጠበቃል።

አገራችን የወንበዴዎች መፈንጫ ሆነ እንዳትቀር፣ ሕልውናዋ አደጋ ላይ እንዳይወድቅና በዘርና በቡድን እየተጎተትን መበታተን እንዳይደርስ ፣ ዜጎች ሁሉ የነዚህን ጀግኖች የመስዋዕትነት አርአያ በመከተል ይህን አገር አጥፊ ቡድን ለማስወገድ በጋራ እንዲነሱና እንዲታገሉ በሰደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ ጥሪውን ያቀርባል ። ቀጥሎ ያለውን አጭር ግጥም ለኢመማ ጀግኖች መታሰቢያ እንዲሆን አቅርበናል።

ቢሞትም ሕያው ነው!!

ለራሴ የማይል -ወገን አስቀድሞ፣
መስዋዕት የሚሆን ግፈኛን ተፋልሞ፣
ለተተኪው ትውልድ የሚያስብ አርቆ፣
ከንቱ ውዳሴና የግል ጥቅምን ንቆ፣
በዕምነቱ ከፀና ሞትንም ሊቀበል፣
ሕያው ነው ተግባሩ እሱ ሞተ አንበል።
አፋሽ አጎንባሹ አየን ተበራክቶ፣
ከግፈኛ አብሮ ሊያድር ሆዱን ሞልቶ፣
እንዲህ ባለው ጊዜ እንዲህ ባለው ወቅት፣
ጀግና ሰው ያበቅላል-ያፈራል መሬት፣
ለወገኑ ቤዛ የሆነ ጀግና ሰው ፣
ታሪክ ይዘክራል ቢሞትም ሕያው ነው።

ያለመሰዋዕትነት ነፃነት አይገኝም!!
በጋራ ታግለን ሕዝባዊ ሥርዓት እንገንባ!!

ድምጻችንን ሰጥተን ውሳኔውን ለመቀበል ዠግጁ ነን?

$
0
0

debereselam-medhanialemየሚኒሶታ ደብረሰላም መድሐኒአለም ቤተክርስቲያን አንድ ምራፍ ጨርሶ ወደ ሁለተኛው ሊዞር በ ጣት በሚቆጠሩ ቀኖቶችብቻ ነው የቀረው። አንደኛው ምን ምን አስመዝግቦ አለፈ ቀጣዩስ ምን ምን ይዞ ይመጣል ብሎ ማሰላሰል ካለፈው እንድንማር ለወደፊቱ እንድንሰናዳ የጠቅማል። ታዲያ ባለፉት ሁለት አመታት በየምክንያቱ ሁለትና ከሁለት በላይ ሆነን  በተገናኘንበት ስፍራዎች ሁሉ ከምንወያይባቸው አርስቶች አነዱና ዋንኛው የቤተክርስቲየናችን ጉዳይ ነበር ።-[ሙሉውንለማንበብእዚህይጫኑ]

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live