Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

በዝዋይ የሚገኙ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች መልዕክት አስተላለፉ፤ (የረሃብ አድማ መምታት ጀምረዋል)

$
0
0

ZIWAY PRISONበዝዋይ የሚገኙ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች የተለያዩ ጥያቄዎችን በማንሳት ጥያቄያቸው እንዲመለስ ጫና ለመፍጠር የምግብ ማቆም አድማ ጀመሩ። አድማው ለ3 ቀን እንደሚቆይ ታውቋል፡፡ ጥያቄያቸውም፡-

1ኛ፦ የፖለቲካው ሥነ -ምህዳር እንዲሰፋና የፓርቲዎች በነፃነት የመንቀሳቀስና የመደራጀት መብት ሳይሸራረፍ እንዲከበር፣

2ኛ፦ አፋኝ የሆኑት የመያዶች ህግ፣ የፀረ-ሽብር ህግ፣ የፕሬስ ህግ እንዲሻሩና ነፃ የሙያ ማህበራት ላይ የሚደረገው አፈና እንዲቀም፣

3ኛ፦ በግሉ ሚዲያ ላይ የሚደረገው ማስፈራሪትና አፈና በአስቸኳይ እንዲቆምና የፕሬስ ነፃነት ሳይሸራረፍ እንዲከበር፣

4ኛ፦ የመከላከያ፣ የፖሊስና የደህንነት አካላት በህገ መንግሥቱ መሠረት የተሰጣቸውን ኃላፊነት በገለልተኝነት እንዲወጡ፣

5ኛ፦ ፍርድ ቤቶች፣ የምርጫ ቦርድ፣ የህዝብ ሚዲያው ነፃና ገለልተኛ ሆኖ እንዲዋቀር፣

6ኛ፦ የፖለቲካ እስረኞች፣ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና የህዝበ ሙስሊሙ ተወካዮች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ፣

7ኛ፦ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ እስር ቤቶችን በተመለከተ፡-

ሀ) የሰብአዊ መብት ጥሰትን የፈፀሙ ማለትም በድብደባ አካል ያጎደሉና በድብደባ የሰው ህይወት ያሳለፉ የተቋሙ አባላት ህግ ፊት እንዲቀርቡ፣
ለ) በደረቅ ወንጀል ለታሰሩ እስረኞች የሚደረግ ዝውውር፣ ይቅርታ፣ ምህረት እና አመክሮ ህግ በሚፈቅደውና መድሎ በሌለበት ሁኔታ እንዲፈፀም፣
ሐ) በሁሉም እስር ቤቶች ውስጥ ‹‹ጨለማ ቤት›› በመባል በሚጠሩት የብቻ እስር ቤቶች ውስጥ የታሰሩ እስረኞች ከጨለማ ቤቶቹ ወጥተው ከሌሎች እስረኞች ጋር እንዲቀላቀሉ።
መ) የምግብ፣ የውሃ፣ የአልባሳት፣ የግል ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች አቅርቦት በአስቸኳይ እንዲሻሻል እንዲሁም እስረኞች ከሚጎበኟቸው ሰዎች በወር የሚፈቀድላቸው 1ዐዐ ብር በቂ ባለመሆኑ ክልከላው እንዲነሳ፣ የመረጃ በነፃነት የማግኘት መብታችን እንዲከበር (ሬድዩ የማዳመጥና የግሉ ሚዲያ ውጤቶች የሆኑ ጋዜጦች እንዲገቡልን) የርቀት ትምህርት መማር እንዲፈቀድ፣ ከውጭ የሚላኩልንን ፖስታዎች በአግባቡ እንዲደርሱን።

8ኛ፦ በህገ መንግሥቱ አንቀጽ 28 ላይ በተደነገገው መሠረት በሰው ልጆች ላይ አሰቃቂ ድብደባና አካል ማጉደል ወንጀል መሆኑን በመፃረር በሀገሪቱ ያሉ የምርመራ ጣቢያዎች በተለይም በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ (ማእከላዊ) ውስጥ ይህንን ወንጀል የፈፀሙና እየፈፀሙ ያሉ የፖሊስና የደህንነት አባላት ለፍርድ እንዲቀርቡ።

9ኛ፦ በሀገራችን ያለውን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ምስቅልቅል በዘላቂነት ለመፍታት መንግሥትና ተቃዋሚ የፖለቲካ ኃይሎች ብሔራዊ መግባባትና እርቅ እንዲያወርዱ። በመጨረሻም በአሁኑ ወቅት ሀገሪቱ ያለችበትን አሳሳቢ ሁኔታ በአግባቡ በመረዳት ልዩነትንና ህልውናን ጠብቆ ለጋራ የነፃነት አጀንዳ በጋራ ተባብሮ መታገል የወቅቱ ዋነኛ ጥያቄ በመሆኑ የሀገሪቱ የፖለቲካ ኃይሎች ሁሉ ተባብረው እንዲታገሉና የኢትዮጵያ ህዝብም ከጎናቸው እንዲቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን። በመጨረሻም ከዚህ በላይ በዝርዝር ያቀረብናቸው ጥያቄዎች ተገቢውን ትኩረትና ምላሽ ያገኙ ዘንድ ለጊዜው ስማችን ከዚህ በታች የተዘረዘረው የፖለቲካ እስረኞች ከአርብ ሚያዚያ 24 ቀን እስከ እሁድ ሚያዚያ 26 ቀን የሚቆይ የ3 ቀን የረሃብ አድማ አድርገናል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

1ኛ አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር
2ኛ አቶ ደረጀ አበበ
3ኛ አቶ ናትናኤል መኮንን
4ኛ አቶ ክንፈ ሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ)
5ኛ አቶ አንዷለም አያሌው
6ኛ ሻ/ል የሽዋስ ይሁንአለም
7ኛ አቶ ምትኩ ዳምጤ
8ኛ አቶ አበበ መልኬ
9ኛ አቶ ማንደፍሮ አካልነው
1ዐኛ አቶ ገበየሁ ብዙነህ
11ኛ አቶ ዩሐንስ ተረፈ
12ኛ አቶ መሠለ ድንቁ
13ኛ አቶ ፍቃዱ ባሳዝን
14ኛ አቶ የገባው አለሙ
15ኛ አቶ እሱባለው አሌ
16ኛ አቶ ጥላሁን ባለው
17ኛ አቶ አስቻለው አራጋው
18ኛ አቶ በእውቀት ደሳለኝ
19ኛ አቶ ካሳሁን ጌጡ

ግልባጭ
- ለኢትዮጵያ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች በሙሉ
- ለተባበሩት መንገሥታት ድረጅት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን
- ለአውሮፓ ህብረት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን
- ለአሜሪካ መንግሥት የውጭ ጉዳይ መ/ቤት
- ለአፍሪካ ህብረት የሰብአዊ መብት ኮሚች
- ለ Human Rights watch
- ለ Amnesty international
- ለ CPJ እና ለሀገር ውስጥና ለውጭ የሚዲያ ተቋማት በሙሉ፡፡

↧

↧

የነፃነት – ቃና። (ከሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 02.05.2014 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

pic2የነፃነት ቃና የነገሮች ሳይሆን ይልቁንም ሰው የመሆን ልዩ ቃና ነው። ቃና መሆን እራሱ ሲያንሰው ነው – ለነፃነት። ነፃነት ትርጉም ያለው መኖር ማለት ነው። መኖር ሲተረጎምም ነፃነት ማለት ይሆናል። ነፃነት እንደ ጎረቤት ሳይሆን እንደ እራስ ሆኖ መኖር የሚያስችል ቀለማም የመብት ባላቤትነት ልዩ እርስተ – ጉልት ነው። የህይወትም እርእስም። ነፃነት ውስጥን ፈቅዶ የመተርጎም አቅም ካለምንም ተጽዕኖ ወይንም ፈቃድ ሰጪ ኃይል ወደ ተግባር ለመተርጎም የሚያስችል የብቃት ብቸኛ ማውጫ ነው። ነፃነት እራስን እንደ ፈለገ ገልጦ አንብቦ መኖር ማለት ነው። እርግጥ ነፃነት ጣሪያና ግድግዳ አለው። መብትና ግዴታ። መብትን ለማግኘት ግዴታን መወጣት። ግዴታን ተወጥቶ የመብት ባለቤት መሆን። ቀደምቶቹ የመብታቸውና የግዴታቸውን ጣሪያና ግድግዳ በአግባቡ ስላወቁ ነፃነታቸውን ለማግኘት ተሰዉ። በነፃነታቸውም በሀገራቸው ዳር ደንበር በወጥ ማንነት ኮርተው ኖረው – አለፉ። ዬድርሻቸውን ዬተወጡት አይደለም እናት ኢትዮጵያን አፍሪካን በአለም የተበተነው የዘረ ጥቁር ተፈጥሮ በተግባር አነጠሩት። መወደሱን ለማንነት በፈቃድ ሸልመው ዙፋኑን ጭነው  -አነገሡት። ኑሯቸው ህይወት — ማለፋቸውም ሕይወት ሆነ። መፈጠርን – ተጠበቡበት። አይደለም ትናንት ዛሬም በራስ የመተማመን ጥገትን በውስጣችን በደማቸው አተሙ። – ብሩካኑ በኢትዮጵዊነት የተካኑ።

የአውሮፓ ቅኝ ገዢዎች ጥሬ ሀብትን ብቻ ሳይሆን እርካሽ ጉልበትን ለማጋበስ አፍሪካን እንደ ቅርጫ በተከፋፈሉበት ዘመን አባቶቻችንና እናቶቻችን በከፈሉት የህይወት መስዋዕትነት ሰውነታችን ተከብሮ እንደ እራሳችን በጣዕማችንና በጠረናችን እንኖር ዘንድ አስቻሉን። ነፍሳቸውን ኤልሻዳይ አርያም ገነት ያስገባለን። አሜን!  የትጉኃኑን አቨውን ዘመን የባረከ አምላክ እኛምንም በበረከቱ ይጎብኘን። አሜን! የቀደሙት የኢትዮጵያ መሪዎች እርብኝነታቸው ከዘመኑ ብቃት በላይ ስለነበረ ከባርነት ያወጡን የነፃነት አባቶቻችንና እናቶቻችን ናቸው። ደግመው ወለዱን – ለክብር።

ኢትዮጵያ ሀገራችን በታላቅ ክብር ከአፍሪካ ተለይታ እንድትኖር ካደረጉት የተግባር ተጋድሎዎች አንዱ እናት ሀገራችን ኢትዮጵያ የራሷ ብርቅና ውድ የፊደል ገበታ ያላት መሆኑ ነው። ይህ ዕጹብ ድንቅ ገቢራዊ ቅርስ እኛነታችን ከሰጡን ታላቅ ባላውለታዎቻችን ደምና አጥንት መስዋዕትነት ውስጥ የተገኘ ልዩ ጥሪታችን፤ የጋራ የመንፈስ ሃብታችን ድህነታችንም ነው። ምልክታችን፤ እኛነታችን ነው።

አማርኛ ቋንቋ ቃናው ነፃነት፤ ጣዕሙ ደግሞ ታላቅ የዕውቀት ዘርፍ ነው። አያሌ ሰዎች የሚስማሙበት ቋንቋ መግባቢያ ነው ብለው ነው። ለእኔ መግባቢያ ብቻ ሳይሆን ቋንቋ የዕውቀት ዘርፍም ነው። ዬዓለም የመተንፈሻ ሳንባዋ ቋንቋ ነው። ቋንቋ ሙያም ነው። ባህልን ወግን ልማድን እምነትን ማንነትን ቀምሮ እራስን መግለጽ የሚያስችል የሀገር አንበደት ነው – ቋንቋ። የህዝብ ልሳን ነው። ቋንቋ ተቋምም ነው። እንደ ኢትዮጵያ ላላ ለታደለ ሀገር ደግሞ የነፃነት በኸረ ልጅ ነው።

አማርኛ ቋንቋ ያደገ፣ የሰለጠነ – ብልህ ወታደር ነው። እናት ሀገሩን ከነፃነት የታደገ ታላቅ ባለውለታም ነው። ጠላትን ቀጥቶ ለማንበርከክ ወጥ አንደበት ባይኖር ትጥቅና ሥንቁ፤ ፍላጎትና ራዕዩ የባቢሎን ግንብ በሆነ ነበር። ሥልጡኑ አማርኛ ግን ግዳጁን በከፍተኛ ደረጃ የተወጣ ሰማዕት፣ አርበኛና አደራ አውጪም ነው።

pic1አማርኛ ቋንቋ ፍሰቱ – ርባታው – ለዛው – ቃናው – ጣዕሙ – ዜማው – አወራረዱ ሳቢና አጓጒ ነው። አማርኛ ቋንቋ ውበቱ ልዩ ነው። ደማም – ዓይነ – ገብም። እያንዳንዱ ነጠላ ፊደል ቅርጽና ይዘታቸው ተደላድለው የተፈጠሩ እንደ አራስ ልጆች ታይተው የማይጠገቡ ብርቅ የዓይን አበባዎች ናቸው።  በሌላ በኩል አማርኛ ቋንቋ አንባሳደራችንም ነው። ከአፍሪካ የተለዬች ኢትዮጵያን ያደረጋት ታላቁ ሚስጥር ቀለማሙ የፊደል ገባታ ሥህናዊ ተፈጥሮ ነው። ለላቀው ብቃቱ ዘመንን እዬሸኜ ፈተናን እዬረታ፤ ጠላቶቹን እያስተማራ አምሮበት አለ። ባሰኜው ቀለም በሀገሩ ወግና ልማድ ትውፊትና ማንነት ፈክቶ  - አብቦ አለ። መፈጠርስ እንደ አንተ-  መኖርም እንደ አንተ – ማወቅም – ማደግም እንደ አንተ፤ መማርም መመራመርም እንደ አንተ -  ባለ ግራጫ ግን ሁል ጊዜም ዕንቡጥ።

የጹሑፌ መግቢያ ፎቶ በ2012 ዓለም ዐቀፍ የፊደላት ቀን ሲከበር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተመረጡት ፊደላታ ጋር አማርኛ ቋንቋ ቤተኛ ሆኖ ፍላየሩ ውስጥ ነበር። ይህ ሁለተኛው ፎቶ ደግሞ እነዚህ የምታዮዋቸው ፊደሎች ለናሙና የተሰሩ ናቸው። ከተመረጡት ዬ17 ሀገሮች የፊደል ገበታዎች ውስጥ አንዱ የእኛው ጀግና ነበር። ይህ ለአንድ ወር በዘለቀው ኤግዚቪሽን መክፈቻ በር ላይ የነበረ ሲሆን „የገደል ማሚቶ“ በሚል እርእስ ሥር በተመረጡት ቋንቋዎች ተተርጉሞ በአንድ መጸሐፍና በድምጽም ንባቡ አብሮ ተያይዞ ቀርቦ ነበር። የአግዚቢሽኑ በር ሲከፈት ደግሞ ውስጡ  ሃብታችን በተሟላ መልኩ ነበር። ለዚህ ክብርና ዝና እንዲህ ያበቁን ኢትዮጵያዊነታችን እንድንሳሰለትና፤ እንድናደንቀው ያደረጉት ቀደመቱ ማስተዋሉን ፈጠሪ አምላካችን አብዝቶ የሰጣቸው ቀንዲሎቻችን ነበሩ።

„የእኛ ታሪክና የፖለቲካ ውጥንቅጥ“ ዲያቆን ኒቆዲሞስ እርቅይሁን ተችተው አኔን እንደጻፉኝ ኢትዮጵያዊነቴ ተጭኖኝ ሳይሆን ሙሉዑ ሰው እንድሆን በደም ፍሳሽና በአጥንት ክስካሽ የተሰጠኝ ውስጤ  - ብርቄም – የመኖሬ ስዋሰውም መኖሬም በመሆኑ ነው።

ለነገሩ እንደ ጸሐፊው አገላለጽ ወቀሰው ለእኔ ክብሬ በመሆኑ ለዚህ የወቀሳ ምስክርነት ላበቃኝ አምላክ ክብር ምስጋና ይግባው። እንኳንስና ይሄ በኢትዮጵያዊነቴ ምክንያት በድንጋይ ተደብድቤ እንድሞት ቢወሰንብኝ እዬዘፈንኩ የምቀበለው ስለመሆኑ የጹሑፌ ታዳሚነታቸውን ስለገለጹልኝ ለክቡርነታቸው ሆነ የእሳቸው ጹሑፍ ታዳሚ ለነበሩ ቅኑ ወገኖቼ አበክሬ በተደሞ መግለጽ እሻለሁ። አሁንም የሰው ሰው መሆኔን የሰጠኝ ኢትዮጵያዊነቴ ክብር -ምስጋናና – ልዕልና ለምንጊዜም እመኝለታለሁ።

pic3በተረፈ መልስ መጻፍ ያለስፈለገኝ ምክንያት ከቅርንጫፍ ጋር ሳይሆን እኔ ከግንዱ ጋር ስለሆነ ግብግቡ ግንዱን ወዳጄን ተክሌሻን እዬጠበኩ ነበር። እምለው ከኖረኝ የታናሼ ቃና የብዕር ውበት ግጥሜ ስለሆነ ደስ እያለኝ ከተክሌሻ ጋር እንጂ ከሌላ ጋር እእ! በተረፈ ሰማዕታት አማርኛ ቋንቋን እስከነ -ሙሉ ትጥቁ፤ እስከነ – ስንቁ ስለሸለሙኝም ዱዳ ሳልሆን ምንም እንኳን በሥነ -ንግግር ጥበብ  ዕድሉን አግኝቼ በሥልጣና ክህሎቴ ቢታገዝም በተፈጥሮዬም ብቁ ተናጋሪ፤ የወጣልኝ አድማጭ፤ ጸሐፊ፤ ገጣሚና ባለቅኔ እንዲሁም በትሁት እርግጠኝነት፤ በፈካ በራስ የመተማመን ስሜት እንዲኖረኝ አባቶቼና እናቶቼ ስለ አደረጉ አውዳቸዋለሁ፤ አከብራቸዋለሁ።  ስለዚህም በሙሉ ሰውነት አለምን በግልቡ ሳይሆን ከልቡ ገብቼ እንደፈትሽው በሚገባ ጠርበው ቀርጸውኛል። ጌጦቼ – ዋርካዎቼ  - ጉልላቶቼ ቀደምቶቹ የነፃነት ሊቀ – ሊቃውንታት።  http://www.ethiomedia.com/14news/our_complex_history.pdf

 

አሁን ወደ ቀደመው — ሁላችሁም እንደምታወቁት ሲዊዘርላንድ የሥራ ቋንቋዎች አራት ሲሆኑ ሶስቱ ጎልተው የወጡ በመሆኑ ዕርእሱ የአምርኛ ፊደል የሚለው በጀርመንኛ፤ በጣሊያንኛና በፈረንሳይኛ ሲሆን … በጎን ያሉት ደግሞ ሲጻፍ ከቀኝ ወደ ግራ እንደሆነ፤ ሲነበብ ከቀኝ ወደ ግራ ስለመሆኑና ከላይ ወደ ታችም እናት ፊደልን ማንበብ እንደሚቻል ተብራርቷል፤ ዝቅ ብሎ የእናት ፊደሎችና የልጅ ፊደላት እርባታን ለአብነት ተስርቷል። ከዚህ ባለፈ ስለ ቋንቋው አጠቃላይ ዜማዊ ድምጸት፤ ስለ ሰዋሰዋዊ ፍሰት፤ ግሳዊ እርባታ፤ የአናባቢና ተነባቢ ፊዳላት ጠባያት፤ በሌሎች ቋንቋዎች የሌሉ ፊደላትና የድምጽ ተዋፆዖ፤ የትውስትን ቃላትን ብቻ ስለሚያስተናግዱት ሁለት ፊደላት ማለትም „ጰ እና ፐ“ እና  የአማርኛ ቋንቋ ፍጥረቱ – እድገቱ – ደረጃውና የወደፊት ዕጣውን በሚመለከት ሰፊ ገለጻ / ፕረዘንቴሽንም / ነበር …. ይህ ብቃት ምንጩ የዛሬ አይደለም የትናንት ዓይነታ ሃብት እንጂ። አንገትን ቀና አድርጎ፤ ልብን ነፋ አድርጎ፤ እኛ አራሳችን የፊደል ገበታ አለን የሚስብል ጉልበታም ፕላኔት በመዳፋችን አለን። የማንም የትውስት ወይንም የብድር ያልሆነ፤ ተሸብቦ ወይንም ተሽበልብሎ ወይንም ተኮፋትሮ ወይንም ተትርትሮ ሳይሆን እራሱን ገልጾ፤ ብቃቱን ሊያሰጎበኝ የሚችል የሊቀ ሊቃውንታት ዕውቀት ጭማቂ ማለት አስችሎናል …. የነፃነት ባለቃናውን ዬአማርኛ ቋንቋ።

 

አማርኛ ቋንቋ ጥልቅ የመሆኑን ያህል አተረጓጎሙ እኔ ነኝ ካለ የቋንቋ ፊደላት ሆነ ሥርዓተ – ህግጋት ቢበልጥ እንጂ የሚያንስ አንዳችም ነገር የለውም። የቀደሙት ከፊደል ቀረጻ ጀምሮ የሠሩለት ሥርዓት አማርኛን እራሱን አስችሎ ቀጥ አድርድርጎ አቁሞ ዓዕምድ እንዲሆን አስችሎታል። አማርኛ ቋንቋ ምርኩዝ – ከዘራ አይሻም። ወይንም ደንበር ዘለል ኩባንያዎች አይለማመጥም – ክፉሉ አይደለምና። ተፈጥሮውም አይፈቅድለትም። ነፃነትን አምጪው ኃይል እራስ በመሆኑ ይህንንም ጀግናው በቃና እና በቅኔ፤ ብብቃትና በስልት – ከውኖታል።

pic1

ሲወዘርላንድ በዙሪክ ክፈለሀገር ቪንተርቱር በሚባል ከተማ በቀን 2000 እንግዶችን በፍቅር የሚያስተናግደው የኢንተግሬሽን እና የህዝብ ቤተ መጸሐፍት የሚገኝበት ህንፃ ከሦስት መቶ ዓመት በላይ የኖረ በመሆኑ ካቩ ሆነ የጣሪያው እንጨት እንደተፈጠረ ውበቱ ከሩቅ ይጠራል። ከላይ ወደ ታች ፍላዬሩ ተሰርቶ ስለነበረ ታሪካዊ ህንጻ ጣሪያውንም ስለሚያሳይ እንዳለ ማቅረቡን መርጫዋለሁ።  „ወ ና ጀ“ ይታያሉ። ስታተልቁት ደግሞ ሌሎችም ይወጣሉ።

 

አማርኛ ያማረ የተዋጣለት ትዕይንታዊ ኪናዊ ቋንቋ ነው። አማርኛ ለፍቅርም ምቹ የሆነ ጣዕም አለው … ሥንኞቹ ዓይናማ ናቸው። ግጥሞቹ ኮልኮዮች ናቸው፤ ቅኔዎቹ ውስጥን ያስነብባሉ  - ርቀው ሊቅነትን ይሸልማሉ። ድርሰቶቹ ተሳለሙኝ ባዮች ናቸው። ተረትና ምሳሌዎቹ ዕውደት ይናፍቃቸዋል፤ ሥነ ቃሎቹ ትውፊትን ይጣራሉ። ቅጽል፤ መስተዋድድ፤ ተወሳከ ከግሥ፤ መስተጻምር ግሥ – ያነግሳሉ።  አደብ የገዛ አደብን ያበረከተ – እጬጌ!

አማርኛ ቋንቋ እራሱን ሲገልጽ በነፃነት ነው። ነፃነቱን የሰጠው እሱ እራሱ ነበር። ነፃነቱን አምጦ አርበኞችን በአኃቲ ልቦና በፍቅር ገዝቶ ባዕቱን አስከብሮ እሱም ከበረ። ቋንቋው የሚርቅ ሳይሆን አቅርቦ እርስዎን እዬፈታተሸ እሱ ደግሞ በተራው በህግ ሥርዓቶቹ ይፈትሽዎታል። ዘንበል ያሉ ግድፈቶችን ትህትናን ለግሶ እያባበለ፤ እያቆላመጣ ያስተምራል።

pic4ባልተወለዱን፣ በቀለም በማንገናኛቸው ዘንድም እንዲህ ይወደዳል። ተከብሮ ያስከብራል። አንገትን ቀና አድርጎ ማንነትን ያበራል። አማርኛ  የኢትዮጵያ ሀገራችን የወል ሃብትና መግለጫ ነው። ንብረትነቱ ግላዊ ሳይሆን እናት ሆዱ በመሆኑ ሁላችንም በእኩልነት ያለአድሎ ያስተናግዳል። ግንኙነታችን የሰመረና ያማራ እንዲሆን ይጓጓል። በዬትኛውም ዘመን የተነሱ ቅኝ ገዢ ፍላጎቶችን ሰብሮ – አዋርዶና – አሳፍሮ የመለሰ የጀግኖች ቁንጮ ነው። ፍላጎታቸውንም አባክኖ ውኃ የበላው ቅል አድርጎታል – አርበኛው።

አማርኛ ቋንቋ በዘመነ ወያኔ በክፉ አይን የሚታይ፤ ስር በሰደደ ጥላቻ ጦርነት የታወጀበት፤ ፍዳውን የከፈለ፤ በረቀቀ ሆኔታ ታቅዶ ሞት የተበዬነበት ነበር። ግን አልሆነም። ወያኔ በፈለገ መልኩ አጠቋቁሮ፤ በባሩድ አቃጥሎ ሊደምስሰው ቢሻም እንሆ ተወደደ ተከበረ ተፈቀረ – ነገም። አማርኛ ቋንቋ ዘመኑ የፈቀደለትን ሥልጣኔ የተቋደስው ከሰማይ በወረደ መና አልነበረም። እሱም ታግሎ ደምቶና ተሰውቶ ነው። ስለዚህ የለመደውን መሰዋዕትነት እንደ ዘምኑ ማስተናገድ የመቻል ሙሉ አቅምና ሥነ – ተፈጥሮ አለው። ለዚህም ነው ገደልነው ሲሉ እያሻተ የሚሄደው፤ አጠፋነው ሲሉ እያሰበለ የሚገኘው፤ ደመሰስነው ሲሉም ቀድሞ ድል ላይ የሚፈርሸው፤ ሊከተክቱት ባዘጋጁት ገጀሞ እንሱን እዬከሰከሰ የሚያሸንፋቸው። ወያኔ ሰው በማያውቀው ደረጃ በጣም ብዙ ነገሮች ነው በአዲስ አባባ ዩንቨርስቲ እንዲከስሙ ያደረገው። ግን ሥራዬ ብለን ተግተን የምንታገልለት ኃይሎች ስላላን ምን አልባት አንድ ቀን የአፈኑት የኢጎ አርበኞች ሲበኑ ሌላም ታእምር ወያኔ ያያል።

አዎን ቋንቋችን አማርኛ ማደግ ስላለበት ዘመኑን የቀደሙ ተግባራት ተከውነውበታል። ትናንት ሲዊዘርላንድ ላይ ጄኔባ ድብልቅ ያሉ ሁለት ፍሬ መጸሐፍቶች፤ ቪንተርቱር ላይ ሙዚዬም ቤተ መጸህፍት ሁለት የአዲስ አባባ ዩንቨርስቲ የሥነ ቃል ጥናታዊ ወረቀቶችና አንድ የሥነ ቃል  መጸሐፍ ብቻ ነበሩ። ዛሬ ግን 6 ጊዜ አስተውሉ 6 ጊዜ በሲዊዝ ብሄራዊ  የኢንተግሬሽን ቤተ መጸሐፍት ብሄራዊ ጉባኤ ስለ አማርናኛ ቋንቋ የአዋቂዎችና የልጆች መጸሐፍት ፍላዬሩን በሀገሬው ቋንቋ እራሳቸው ሰርተው ማብራሪያ ተስጥቶበታል። እናም አብዛኞቹ የኢንተግሬሽን ቤተ መጸሐፍት አዲስ መምሪያ ከፍተው በፍቅር እያስተናገዱት ይገኛል። ትግሉ ይቀጥላላ ውጤቱም ይታፈሳል ……

ሌላም ይታከል – በሥነ ሥርአት፣ በንድፍ የተሰሩት ግጥሞች በቂ ጊዜ ተስጧቸው ለኤግዚቢሽን በቅተዋል። አለ ሌላም ቤተ መጸሐፍት ታዳሚዎቻቸውን የአማርኛ ቅኔ ሲዘረፍ በጣዕማዊ ቃና አስኝቷቸው ውሎ አበሉን ትራንስፖርቱን ክፍለው ቁጭ ብለው አዳማጡት። ይደገምልን እያሉ፤ በመጨረሻም „ የምሽት ማህሌት“ ሲሉ አደነቁት።

 

ግን ምን ያደርጋል? እንዲህ በሰው ሐገር የሚደከምለት ወያኔም በአንጡራ ጠላትንት ፈርጆ የሚደቁሰው አማርኛ ቋንቋ ንዑድ መንፈስን የሰነቁትን ማዬትም መስማትም አንሻም ሲሉ የኢጎ አርበኞች በዬኑበት።  አዎን! በ2013 የካቲት 4 ሲዊዘርላንድ ጄኔባ ላይ የኢሳት ፈንድ ራይዚንግ ነበረ። እንዲሸጥ በጊዜ ተጠዬቀ። ፈቃዱን ማግኘት አልተቻለም። ማስታዋቂያ ብቻ መናገር ይቻላል ተባለ። ይህ ስለተባለ ገንዘብ – ጊዜ  - ጉልበት ፈሶ ከእያንዳዱ ለናሙና 3 ሲደምር 18 መጸሐፍት 4 ሰአት ተጓዙ ወገኖቻቸውን ሊዩ – ጓጉ። ያው ከወገኖቹ ጋር ውስጥ ባይፈቀድላቸውም ውጪ ኃይለኛ በረዶ ነበር እንሞክራለን አለችኝ ክብሬና እህቴ ወ/ሮ ምስራቅ መንገሻ ይዘን ሄድን። ይህም አልሆነም። በቃ ይህ ነው የነፃነት ትግል።

እህቴ አረረች ማስታገስ ስለነበረብኝ ወቅቱ ያልነበረውን አዲስ ፕሮጀክቴን ነገርኳትና እንድትረሳው አደረኩኝ። እኔን ነፃ ሊወጣ በተደራጀ ሚዲያ ላይ የነፃነት ቃና ውበት ታሸገ። እኔን ግን አስቆመኝ?! እእ! አንድ ወንድሜ በጥልቀት ያውቃል። እንዲያውም ተጨማሪ ገንዘብ ላኩ „ እንቅልፍ አልባዋ ሥርጉተ ሥላሴ“ እስከ ማለት ያስቻለው የማይታይ ተግባር ከወንኩ። የወጣው ገንዘብ ቀላል አልነበረም። በወቅቱ ዓይኔን ኦፕራሲውን አድርጌም ስለነበር ያልተጋባ እርምጃ ነበር የወሰድኩት። ግን አረመኔዎች ናቸው። ትንሽ ብጣቂ አንጀት ያልሰራላቸው። አሁን ወያኔ ቢሆን ስንቱን ባል ነበር። ለእነዚህ በነፃነት ሀገር ነፃነቴን ለሚነጥቁ  — ለሚጨፈልቁ – ለሚረማማዱበት —- ሰዎች ፍርድና ዳኝነትን ከጌጦቼ ስለላ የቤተ ሥራውን ለእናንተ ልስጥ። አይካድ ነገር ሶስት እህቶቼ – ተሳትፈውበታል። ያውም እኮ እኔ ከሞት የተረፍኩ ነገ ምን ሊሆን እንደሚችል የማላውቅ ነኝ። አይታፈር ስሞትላቸው ለቀብር ይመጡ ይሆናል። „አሻም“ አልፈልግም።

ህም!  እንኳንስ 18 መጸሐፍት ከሁለት ኪሎ በላይ በሃኪም የተከለከልኩ ነኝ። ክብሮቼ  እናት ሆዱ ሁነና ግፍና በደሉን መርምሩት። እግዚአብሄር ይመስገን። አሁን ማስታወቄውን በብላሽ ኢትዮ ሚዲያና ሞረሽ ወገኔ ሠሩት፤ ከዚህ በኋለ ሊንኩን ወገኖቼ በሙሉ እዬተሻሙ ተረባረቡበት። ጭንቀት ነበረኝ አዲስ ሥራ ስለሆነ እንዳልዘረፍ። አሁን ግን መንፈሴ አረፈ።  ዘሃበሻም ማህበራዊ ድህረ ገጽ ደግሞ ቀዳ እያደረገ ልሳኑን በፍቅር ተቀበለ። በጉልበተኛ አቅመ ቢስ ኢጎ ታፍኖ የነበረው በር ቧ አድርጎም ከፈተለት። እንዲህ ተገናኝ እንጂ ተለያይተን እኮ ነበር። ከ2009 እስከ 2014 ብዙ ነው መርግም። ግን ተቻለ። እጅግ አመስግናችኋለሁ። ነፃነትን በእናንተ አዬሁኝ። ለዛውም ለሴት! ድንቅ ነው። ተመስገን! እንኳንም 2011 አልሞትኩኝ።

 

የሰማይን ጸጋ መገደብ አይቻልም – ፈጽሞ። ሥጦታው የመዳህኒት ነውና። የተዘጋ ተከፈተ። ማን ያውቃል ነገ እናንተን ሊይ ወደ እምትኖሩበት ባዕት ብቅ ይል ይሆናል። ሲዊዞች ጣዕሙን የሚለኩትን እናንተም ትቋደሱት ይሆናል። ተክሌሻ ወንድምአለም እዬሰማህ ነው? ለመሆኑ አለህ ከእኔ ጋር ነህን? መቼም እኔ ካለአንተ ብዕር አይሆንልኝ። እስቲ አንድ መላ በል አባቱ። መቼም እኔና አንተ ፍቅር በፍቅር ሆነናል። አንድ ጊዜ የዶር/ አረጋይ መጸሐፍን ተሳታፊው ምጥጥ አደረገላቸው ስትል ትንሽ ዜና ቢጤ አኮምኩመህን ነበር። እዚህ ደግሞ ግልምጫውም ጥፊውም ተችሎም ጋዳ ነው – ተራራ። ገደሉኝ ስልህ! በሽታሽቶ።


ሲዊዝ የአንድነት ድጋፍ ድርጀት እናት ድርጅቱ እውቅና እንዲሰጠው ያልታከተ በሳል ጥረት አድርጎ አልተሳካለትም። ሲዊዝ ውስጥ ያለው ትሬኮላታ ታገለው። በመጨረሻ አባላቱ ተዘርፈው የሀቅ አርበኞች ተገፈተሩ። ሲዊዝዬም ከአንድነት ረድኤት ውጪ ሆነች። ሥርጉተን የተከላት ኢሠፓ ፓርቲዋ ነው። ያበቀላት ደግሞ ገበረመድህን በርጋ ነው። ገብረመድህን በርጋ ማለት ጎንደርን ፓሪስ የማድረግ ንዑድ አቅም፤ ኢትዮጵያን የመሥራት ጥልቅ ጥበብ የነበረው፤ ትውልድ ሊተካው ከቶውንም የማይችል የድርጅት ናሙና  ነበር። ስለሆነም ሥርጉተን ጠቅላል አድርጎ ቆሻሻ ውስጥ መጨመር አይቻልም ቁርጠችሁን እወቁ – ።

ቅኑ ጎጄ ወንድሜ መከፋትህን ጥቃቴ ውስጥህ እንደ ገባ ጥቅምት 12.2013 ዙሪክ ላይ ሳገኝህ  በአይኔ አይቻለሁ። ዬአንተን ፈቃድ ስለሟላሁ፤ ሁለት ጊዜ ሙሉ በራሴ ወጪ ፍርንከፈርት አማይን በግንቦት 7 ስብሰባ መገኘቴ የተከለውን ቋሳ በምልሰት ትመረምረው ዘንድ በአጽህኖት አሳስብኃለሁ። ለእኔ አይደለም ለነፃነት ትግሉ አይበጅም። አፋፍ ላይ የተንጠላጠለ፤ በብዙ ዝንቅ ፍላጎት የታመለ ስሜት ይዘን የታላቋን ኢትዮጵያን ህልም መመኘትም ጅልነት ይመስለኛል።

ሌላው አስደሳቹ ዜና ስለ ፍቅር ሥርጉተ እምትለው ስለነበራት አሁንም 7ኛው መጸሐፏ መንገድ ላይ ነው //// 8ኛውም እርማት ላይ ነው – ይቀጥላል በዚህ በያዝነው አምት //// ሌላም ስለ አማርኛ ቋንቋና ስለ ኢትዮጵያ መታዳም ሰሞኑን ትንሽዬ ቀዳዳ አግኝቻለሁ። ተመስገን! እግዚአብሄር አብሮ ካለ ሁሉም አለ። የሰማይን መክሊት ከቶ ማንም ሊገድበው አይችልም …. ገና ያፈራል  - ይጎመራል። ወርቅ ይፈልቃል እንጂ አይማርትምና። አማርኛ ቋንቋ ቤቱ ውስጥ ሆኖ ውስጥነቱን ያዘራል። ሥርጉተም ትግሏን በመቀጠል ታንቆጠቁጠዋለች። የተደራጀው አደራጅ ግጥሙ ነውና።

 

የሚገርማችሁ ነጮቹ ይወዱታል አብሶ ለፊደልና ለተስፋ መጸሐፍት  ፍቅራቸው ጥልቅ ነው። ስለሆነም በጉባኤዎች፤ በኤግዚቢሽኖች በገለጣ ጣቢያዎች ከነፃነት – ቃናችን ጋራ ይገናኛሉ – እኛስ ነው ጥያቄው? ግን 613 ግጥሞችን በሶስት መድብል በአንድ ጊዜ አፍ ባላው የመቃብር ኑሮ  - ያሳተመ ሰምታችሁ ታውቃላችሁን? ሥርጉተ በ2010 አድርጋዋለች። በ2012 በአንድ አመት ብቻ ሶስት መጸሐፍትን አሳትማለች። „የሥርጉተ ሥላሴ የመንፈስ ሰብል።“ ይህቺን ቃል ጉግልን ብታጎርሱት ይነግራችኋል። ጉግል ጉቦ ይወዳል። ታዲያ ጉርሻው እንደ „ባለታክሲው ፊልም“ በቢላዋ እንዳይሆን አደራ! ብረት ግጥሙ አይደለም። በዘንካታ እጣት። ጉግልንም ባህላችን እናስተምረው – ይሁን በሉ።

 

እንደ መደምደሚያ – ቋንቋ ሰው ሰው የሚሸት ቃና እና ናርዶስ አለው። ቋንቋ ጌጥ ነው – ልዩ። ውስጥን የሚሳይ ዘመናዊ መስታውት ነው። ስለ ውስጥ የሚናገር ርትዑ ነው። ቋንቋ ከተናጋሪው ቀድሞ ተናጋሪውን የማንበብና የመተርጎም ጸጋ አለው። ቋንቋ ንዑድ መንፈስ ስላለው ርህርህናው ጥልቅ ነው – እርግብ። እኔ „እኔን“ ከምገልጸው በላይ በተብራራ መልኩ አማርኛ ቋንቋ „እኔን“ ተርጉሞኛል ብል ግነት አይደለም።

 

የኔዎቹ ጨረስኩኝ። ዕለተ ሃሙስ ያው በተለመደው ጊዜ የቻላችሁ አዬር ላይ፤ ያልቻላችሁ ደግሞ አርኬቡ ላይ ግንቦት 8. 2014 እንገናኝ። www.tsegaye.ethio.info Tsegaye – Radio Lora Aktuelles ወይንም www.lora.ch.tsegaye ብዕሬን ብቻ ሳይሆን እኔን እህታችሁን ናፍቆት ብትክትክ አድርጎ ሲነዳድለኝ ታዳምጣላችሁ። ጀግኖቻችንም አብረን እናከብራለን። ጀግናን አብረን እንናፍቃለን …. እሺ ….. መልካም የንባብ ጊዜና ሰንበት ተመኘሁላችሁ እኔ ሎሊያችሁ ሥርጉተ ሥላሴ።

 

  • ፎቶዎቹ የተገኙት ከሲዊዞች ጋራ ስለተሰራ ነው እንጂ በተለያዬ ሁኔታ ከኢትዮጵውያን ጋር የተሰሩ ቪዲዮዎች ፎቶዎች ማግኘት አልቻልኩም – እንኳንስ አኔ በሚቀርቧቸው ሰዎች እንኳን ተሞክሮ አልተቻለም – ጉበልበተኞች። ተዳፈን። እረመጥ ነው ፍሞ ያበስላለ …..

 

 

ነፃነት የገባው ማንነት ለነፃነት ክብር አለው። ግን ማንነቱ እራሱን ማግኘት ከቻለ ብቻ!

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

 

↧

የማለዳ ወግ … እነሆ የጨለመው ነጋ ! … ነጻ ወጣሁ ! አመሰግናለሁ (ጋዜጣኛ ነብዪ ሲራክ)

$
0
0

ነቢዩ ሲራክ

እነሆ 60 ፈታኝ የመከራ ቀናቶች በትዕግስት ተገፍተው አለፉ ፣ ክፉውን ቀን ለማለፍ የትዕግስት ጽናት ብርታት ተስፋየ ምንጩ በመላ አለም የምትገኙ ወገን ወዳጆቸ ነበራችሁና ላደረጋችሁልኝ እና ላሳያችሁልኝ የሞራል ድጋፍ ልባዊ ምስጋና አቀርባለሁ ! አሰልችውን ቢሮክራሲ አልፈው ፣ በማይጨበጠው ቀጠሮ ሳይሰላቹ ሌት ተቀን እኔን ሀፐነው ታመው ጉዳዬን ለምስለኔ አቅርበው ድቅድቅ ጨለማው እነወዲገፈፍልኝ ያደረጉትን ለማመስገን ቃላት ያጥረኛል ! ለደህንነታቸው ስል በስም ለማንሳት የማይቻለኝ ወንድሞቸ ብርታት ፈጣሪ ታክሎበት ለዛሬው ንጋት ደርሻለሁ ! ተመስገን ! ነግቶም በአይኔ ሲንቀዋለሉ ከነበሩት ብላቴና ልጆቸና ከመላ ቤተስብ ዘመደ አዝማድ ጓደኛ አፍቃሪዎቸ ለመገናኘቴ ምክንያት እናነተ በአካል ከጎኔ የቆማችሁ ነበራችሁና በሁሉም ስም ምስጋና ወደር የለውም !Nebiyu Sirak

ከማዕከላዊው የብሪማን እስር ቤት ወዳጆቸ …በብሪማን ያላፉ ኢትዮጵያውያን የህግ ታሳሪዎች መካከል በግፍ የታሰሩት አሰገራሚ ታሪኮችን ከእናንተው ጋር በአካል ተገኝቸ ” እህ ” ሰምቸ ተምሬባቸዋለሁ ። በእስር ቤቱ ታዛ እና ግድግዳዎች ላይ የጻፏቸው ማስታወሻና ጥቅሶችን ተመልክቸ ተጽናንቸባቸዋለሁ ። አንዷ ተደጋግማ የሰማኋት ጥቅስ ውስጥ እኔም በመከራው ሳልፍ ተስፋን ሰንቄ እዚህ ደርሻለሁ! ” እኔ መውጣት የምፈራው መውጣት ከማልችለው ከመቃብር እንጅ ፣ መውጣት ከምችለው የብሪማን ወህኒ አይደለም! ” ትላለች ! አዎ ያ ቤት መቃብር አይደለም … በተስፋ ኑሩ ! አካላችሁ እንጅ አዕምሯችሁን ማሰር የሚቻለው የለምና ብሩህ ተስፋን ሰንቁ ! ፍትህ ርትዕ የጎደለባችሁን ድምጽ ዛሬም እንደ ትናንቱ ለምሰለኔዎቻችን አሰማለሁ ! አይዟችሁ !

ለእነ እንቶኔ መረጃ ቅበላየን ጠልታችሁ ላሳደዳችሁኝና ላልተሳካላችሁ ! ” ወደ ገደል አፋፍ ገፋነው ! ” በትምክህት የታበያችሁ ፣ ህልማችሁ ያልተሳካ እኩዮችም ቢሆን ያለመታከት በመስራታችሁ በመንገላታቴ አልተጎዳችሁኝምና ደስ አይበላችሁ ! እግሬና እጆቸ በካቴና ታስረው ወደማላውቀው የወህኒ ህይወት ስወረወር የማላውቀውን አውቄ ፣ ተምሬና ኑሮ በመከራ እንዴት እንደሚገፋ እማር ዘንድ ምክንያት ስለሆናችሁኝ አመሰግናችኋለሁ ! አዎ ዛሬ ነጻ ወጥቻለሁ !

ያሳለፍኳቸው 60 የወህኒ ቀናት ራሴን አዙሬ እንዳይ አድርጎኛል። በቀረጣይ ቀናት አረፍ በፍጥነት ከሚስገመገመው የመረጃ ቅብብሎሽ አውድ ገለል ማለት ባይቻለኝም ለአፍታ አረፍ ማለትን መርጫለሁ! በቀጣይ እረፍት ቀናቶቸ ወደ ብላቴና ልጆቸና ቤተሰቦቸ ፣ያለፉ እና በውዝፍ የቀሩትን የቀሩ የአረብ ሃገር ስደቱኛ ህይወት ከጋዜጠኝነት ህይዎት ተሞክሮው ጋር አዙሬ እመለከተው ዘንድ ግድ ይለኛል!

ከአፍታ እረፍት በኋላ እስክንገናኝ ፣ ሁላችሁንም አመሰግናለሁ: )

ሰለም ለሁላችሁ !

↧

በሚኒሶታው መድኃኔዓለም ቤ/ክ ስም መነገድ ይቁም!!! [አቡነ ማርቆስ ቤ/ክርስቲያኑንን አሳማ ያርቡበት ያሉበት አነጋጋሪ ቪዲዮ]

$
0
0

በቀጣይ ያስተናገድንላችሁ መልዕክት ለሰላም እና ለአንድነት ከቆሙ የሚኒሶታ ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ምዕመናን የተላለፈውን ጥሪ ነው።

debereselam Minnesota
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን።
5/3/2014

የቤተክርስቲያናችንን አንድነትና ሰላም ለመናድ እየተንቀሳቀሰ ያለው ቡድን በታላቁ ደብራችን በደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ስም የሐሰት ዘመቻ እያደረገ ስለሚገኝ የቤተክርስቲያናችን አባላትና ሌላውም ኃይማኖቱንና አገሩን የሚወድ ሁሉ እየተነዛ ካለው የሐሰት ቅስቀሳና አሉባልታ እራሱን እንዲጠብቅ እናሳስባለን።

የቤተክርስቲያናችን የሚኖሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የገለልተኝነት አቋም አሁንም ያልተቀየረና የተጠበቀ ሲሆን በቅርቡ የዚሁ የሰላምና አንድነት አፍራሽ ቡድን ዋነኛ አንቀሳቃሽ ከሆኑት ግለሰቦች መካከል አንዱ ወደ ኢትዮጵያ በመሔድ ሥልጣን ላይ ባለው ኃይል 6ኛ ፓትርያርክ ተብለው ለተቀመጡት አባት ሜኖሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አዲስ አበባ ባለው ሲኖዶስ ሥር ለመተዳደር ወስኗል በማለት የተሰራጨው የድምጽና የቪድዮ መልእክት ፍጹም ከእውነት የራቀ እንደሆነ ሁሉም እንዲያውቀው እንወዳለን።

ሰላምና አንድነትን አሻፈረኝ በማለት የቤተክርስቲያኑ አባላት ተሰብስበው የመጨረሻ ውሳኔ እንዳያስተላልፉ መሰናክሎችን ሲፈጥር የነበረው የዚህን ቡድን ሕገወጥ አካሔ በፍርድ ቤት አስገዳጅነት የአባላት ጠቅላላ ጉባኤ ለሜይ 11 ቀን 2014 ዓ.ም እንዲካሔ ከተወሰነ በኋል የሚያደርጋቸውን ሕገወጥ
አካሒዶች መቀጠል ስላልቻለና በጉባኤውም ተሸናፊነቱን አስቀድሞ በማወቁ ራሱን በእለተ ሆሳዕና ከቤተክርስቲያን ለይቷል። በቅርቡ ተወካዩን ወደኢትዮጵያ በመላክም ሕዝቡ ሳይወስንና ስብሰባም ሳያደርግ ሚኖሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በእናንተ አመራር ሥር ለመሆን ወስኗል
በማለት የሐሰት ወሬ ለፓትርያርክ አባ ማቲያስ የተነገረውና እርሳቸውም ያስተላለፉት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ቤተክርስቲያናችንን በማይወክሉ እወደድ ባዮች የተፈጸመ ማወናበድ ስለሆነ ደብራችን ደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አሁንም ሆነ ወደፊት በአባቶች መካከል ያለው መለያየት ተፈትቶ አንድ ሲኖዶስ አንድ ፓትርያርክና አንድ አመራር እስከሚፈጠር ድረስ በገላጋይነት አቋም የሚጸና መሆኑን ለአንድነትና ለሰላም የቆምን ብዙኃን የቤተክርስቲያኑ አባላት ሁሉም እንዲያውቀው በአጽንዖት እናሳስባለን።

ከዚህም በተጨማሪም በበራሪ ወረቀቶችና በራድዮ እንዲሁም በየዌብ ሳይቱና በፌስ ቡክ ቤተክርስቲያናችን ሰባኪያንን እና ዘማሪያንን በማስመጣት ጉባኤ ያዘጋጀ እንደሆነ ተደርጎ እየተላለፈ ያለው ቅስቀሳም ሐሰት መሆኑን እንገልጻለን። የተባለው ስብሰባ የተዘጋጀውና የሚመራውም በዚሁ ራሱን ለእምነትና ለእውነት ሳይሆን ለፖለቲካ መሳሪያነት ባዘጋጀው ቡድን ስለሆነ ምእመናን ጥሪው የቤተክርስቲያን እንዳልሆነ እንዲያውቁት እንወዳለን።

በቤተክርስቲያናችን ችግር በመፍጠር ሰላማችንን የረበሹትን የቦርድ አባላት ሽሮ በምትካቸው አዳዲስ የቦርድ አባላትን ለመምረጥ እና በዲሴምበር 15/2013 በከፍተኛ ድምጽ ቤተክርስቲያናችን ባለችበት የገለልተኛ/ገላጋይነት አቋም ትቀጥል ተብሎ የተወሰነውን ውሳኔ ለማጽደቅ ሜይ 11/2014 በሚደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ድምጽ መስጠት የምትችሉ የደብራችን አባላት ሁሉ በስብሰባው ላይ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በዚህ አጋጣሚ ላለፉት ዓመታት ተከብሮ የቆየውን የእግዚአብሔርን ቤት ይኸው የሰላም እና የአንድነት አፍራሽ ቡድን የጋበዛቸው አቡነ ማርቆስ “ህንጻ” እያሉ ሲያቃልሉትና “አሳማ ያርቡበት” ያሉበትን ቪድዮ በድጋሚ ትመለከቱት ዘንድ፤ ላላዩትም ታሳዩ ዘንድ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። አቡነ ማርቆስ ደብረሰላምን አሳማ ማርቢያ አድርጉት ቢሉም የእግዚአብሄር ቤት የአሳማ ማርቢያ አይሆንም።

ወ ስብሐት ለእግዚአብሔር!

↧

“ኢንሔሊ ተቃርኖተ ጽድቅ” “ከእውነት ጋራ የሚጋጭ ነገር እየሰራን ለመኖር አንድፈር” –ከቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

$
0
0

ቀሲስ አስተርዕየ

ቀሲስ አስተርዕየ

አቡነ ማቲያስ

አቡነ ማቲያስ

nigatuasteraye@gmail.com
ሚያዚያ ፳፻፮ ዓ.ም.

ማሳሰቢያ፦
እንደሚታወቀው ከዚህ ቀደም በተከታታይ ያቀረብኳቸው ጽሁፎች፤ አንባቢ በግልጽ ወደሚያያቸው ክስተቶች ቀጥታ ዘልዬ በመግባት አይደለም። ይህም ባለመሆኑ፤ ከነገረ መለኮት ውስጥ ሳልገባ ህዝባውያን የሆኑትን ነገሮች ብቻ ባቀርብ ላንባቢ እንደሚቀል የተለያዩ ምክሮችና ሀሳቦች ከተለያያችሁ ወገኖቼ ቀርበውልኛል። እንደናንተ ሀሳብ ቢሆን ኖሮ ፤ ላንባቢ ጥልፍልፍ ከሚሆንበት ነገረ መለኮት ከመግባት ይልቅ፤ ወቅታውያን የሆኑትን ነገሮች ብቻ እንደክር በመምዘዝ ለማሳየት በቀለለኝ ነበር። ምክራችሁ ትክክል ቢሆንም፤ ለመቀበል ከዚህ በታች በገለጽኳቸው ምክንያቶች እንደምቸገር ተረዱልኝ።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

↧
↧

ወደ ህሊናችን እንመለስ (አንተነህ መርዕድ)

$
0
0

 

Landindየመሬት ጥያቄ ብዙ መስዋዕት የተከፈለበት ቢሆንም አሁን በባሰ ሁኔታ ወያኔ ከሁሉም ዜጋ ነጥቆ በግሉ አድርጎታል። ማንም ኢትዮጵያዊ የሃገሩ፣ የመሬቱ ባለቤት አይደለም። ከዚህ የባሰ ዜጎችን የማዋረድ ተግባር የለም። አባቶቻችን መሬታቸውን ለባዕድ አንሰጥም በማለት ህይወታቸውን ከፍለው አቆይተውናል። ዛሬ እኛ የራሳችን መሬት ባለቤት እንዳንሆን ሁላችንንም መሬት አልባ ያደረገን ስርዓት ዜጎችን አፈናቅሎ ካድሬዎቹን በመሬት ችብቸባ አሰማርቷል። ለባዕዳን ከመሸጥ አልፎ “እኛም የመሬት ባለቤት ልንሆን ይገባናል” ያሉትንና ይህንኑ የዜጎችን ህጋዊ መብት የጠየቁትን ሁሉ በጠራራ ፀሃይ ባደባባይ ይገድላል።

ጋምቤላዎች፣ አፋሮች፣ ሲዳማዎች፣ ጉጂዎች፣ ሶማሌዎች ዛሬ ደግሞ አምቦዎችና ጎንደሮች የተገደሉት መሰረታዊ የሆነውን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ በማንሳታቸው ነው። በየቦታው እያናጠለ ዜጎችን የሚገድለው የወያኔ ስርዓት በቀነበበልን ጠባብ መንደር ተከልለን ጥቃቱ ወደየቤታችን እስኪመጣ የምንጠብቅ ገልቱዎች መሆናችንን ከብዙ የህይወት መስዋዕት በኋላ እንኳ የተማርን አይመስልም። ትናንት አገራዊ አጀንዳ ይዘው የመታገልና መስዋዕት የመክፈል ታሪክ ያላቸውን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች “የትግራይ፣ የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የሶማሌ…” እያለ ከፋፍሎ በወንድሞቻቸው ላይ የሚደረገውን ጥቃት በጋራ  እንዳይከላከሉ እስከ ማድረግ ደርሷል። አያቶቻችን ከሰሜን ከደቡብ፣ ከምስራቅ ከምዕራብ ተጠራርተው ጠላታቸውን በመከላከል ተደራርበው የወደቁባት ይህች አገር የማን ናት? ኦጋዴን፣ ኤርትራ፣ መተማ ወዘተ. የወደቁ አባቶቻችንን አጥንት የየትኛ ጎሳ አባል እንደሆኑ መለየት እንችላለን?

ከመቶ ዓመት በፊት ተገደሉ የተባሉ ዜጎቻችንን ካረፉበት መቃብር እየተቆፈረ ለፖለቲካ ፍጆታ፣ ለከፋፋይ ዓላማ የሚያናፍሰው ስርዓት በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች ዜጎች መሰረታዊ መብታቸውን በሰላማዊ መንግድ ስለገለጹ ብቻ እየገደለ ነው። ሰሞኑን ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና እንዲሁም የኦሮሞ ፌዴራሊስት አመራር አባላት እንደገለጹት ያለፈ ታሪክ ስህተትን ስንቆፍር አዲስ ኢትዮጵያን በጋራ ለማለም አልቻልንም። ተባብረን አሁን በተከሰተ ችግር ዙርያ እንታገል ሲሉ ያቀረቡት ጥያቄ ተገቢ ነው።

ከሁለቱም ወገን ያሉ ጽንፈኞች የሚያካሂዱትን የጥላቻ ዘመቻ ችላ ብለን አሁን ባለ የጋራ ችግር ዙርያ ትግልን በማቀናበር የምንመኛትን ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያ ለመገንባት መተባበር የወቅቱ አብይ ቁም ነገር ነው።

የሁሉም ኢትዮጵያውያን ህይወት ክቡር ነው። ለንጹህ ዜጎች መሞትና መታሰር ሃላፊ የሆኑትን ሁሉ ኢትዮጵያዊ ሰብአዊ መብት ተቋማት፣አክቲቢስቶች፣ የፖለቲካ ድርጅቶችና ግለሰቦች እየመዘገቡ መያዝ ያስፈልጋቸዋል። ሁሉም በሰራው ነገ ተጠያቂ መሆኑ አይቀርምና።

የኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች ከደርግ አወዳደቅ ለመማር ጊዜው ሩቅ አይደለም። መንግስቱ ኃይለማርያምና ከጥቂት ባልደረቦቹ በቀር አብዛኞቹ ላለፈ ተባባሪነታቸው ዋጋ ከፍለውበታል። ከሁሉም በላይ ግን የህሊና ጠባሳቸው ቀላል አይደለም። አቅፋችሁና ደግፋችሁ የያዛችሁት ስርዓት ተጠቃሚዎችና ወንጀለኞች ጥቂትና በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። ለማምለጫቸው ቦታ፣ ለኑሮአቸው ከፍተኛ ንብረት አሽሽተው የመጨረሻውን ቀን እየተጠባበቁ ነው። እነሱ ሲሄዱ በጠራራ ፀሃይ ልጆቻቸው የተገደሉባቸውን፣ መሬታቸውንና ንብረታቸውን ተነጥቀው የተፈናቀሉን፣ በየእስር ቤቱ በግፍ ሲማቅቁ የነበሩትን፣ ባጠቃላዩም ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ግፍ ሲፈጽምባቸው የነበሩ ኢትዮጵያንን ቀና ብላችሁ ማየት የማትችሉበትና ለድርጊታችሁ ተጠያቂ የምትሆኑበት ጊዜ ይመጣል። ወደ ህዝባችሁ መመለስ ካለባችሁ ጊዜው አሁን ነው።

ሁላችንም ወደ ህሊናችን እንመለስ። እየጠፋ ያለው ነገ አገሪቱን የሚረከቡ ወጣቶች ህይወት ነው። በደርግ ወቅት በእርስ በርስ መጨራረስ ከተሞች ወስጥ ያለቀው፣ በኦጋዴን በረሃ፣ በኤርትራና በትግራይ ጋራዎች የረገፉ ወጣቶቻችን፤ ወያኔ ስልጣን ላይ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ በኢትዮ-ኤርትራ ትርጉም አልባ ጦርነት እንዲሁም በየቦታው የተገደሉ ዜጎች ቁጥር የባከነውም ንብረት አገራችንን አሁን ላለችበት የዓለም ጭራነት ዳርጓታል። ከዚህ በኋላ ሌላ ውድ ህይወትና የአገር ሃብት ማጥፋት የማንኛውም ቅን ኢትዮጵያዊ አላማ አይሆንም። ችግራችን የጋራ ነው። አገሪቱም የጋራችን ናት። የገራ የሆነ አገርና ህዝብ ደህንነት የሚጠበቀው በጋራ ተሳትፎ ነው። ድብቅ አጥፊ ዓላማ ካላቸው በቀር ሁላችንም ለጋራ ቤታችንና ህዝባችን ባንድ እንቁም።

ኢትዮጵያን እግዚአብሄር ይባርክ

አንተነህ መርዕድ  amerid2000@gmail.com

ሜይ 2014

 

 

 

↧

ዓረና ለትግራይ ፓርቲ በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ እየተወሰደ ያለውን የኃይል እርምጃ አወገዘ

$
0
0

Arena-Tigray-logo (ዘ-ሐበሻ) በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች በተለይም በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የኃይል እርምጃ ይቁም ሲል ዓረና ትግራይ ለዴሞክራሲና ሉአላዊነት ፓርቲ አስታወቀ። ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ “በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ በመንግስት ኃይሎች እየተወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ ያውግዛል።” ብሏል።

“ለማንኛውም የህዝብ ጥያቄ መልሱ ግድያ ሊሆን እንደማይችል ያምናል።” ያለው ዓረና “የኢህአዴግ መንግስት የህዝብ ጥያቄዎች በአግባቡ መፍትሔ ከማፈላለግ በኃይል ለመጨለቅ መሞከሩ ካለፈው የደርግ ስርዓት መማር አለመቻሉ ያሳያል።” ብሏል።

“ኢህአዴግ ህዝብን ማስተዳደር ባለመቻሉ ምክንያት የህዝብን ተቃውሞ እያየለ በመሄዱ ስልጣን ለህዝብ የሚያስረክብበት መንገድ ማመቻቸት ይኖርበታል።” የሚለው መግለጫው ሰሞኑን እየወሰደው ያለው የኃይል እርምጃ ባስቸኳይ እንዲያቆም ጠይቋል።

“መላው የትግራይ ህዝብ ከተጎጂዎች ጎን እንዲሰለፍና የኢህአዴግን የኃይል ተግባር በግልፅ እንዲያወግዝ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።” ያለው ዓረና ህይወታቸው ባጡ የኦሮሞ ተማሪዎች የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን ለመግለፅ እንወዳለን።” ብሏል።
6 killo University

↧

ህመሙ የጋራ ሀመም ነው ጩኸቱም የሁላችንም ጩኸት ነው (የአቋም መግለጫ እና ምክር ብጤ!)

$
0
0

ከአቤ ቶክቻው

በአሁኑ ሰዓት በኦሮሚያ ክልል ሁሉም አካባቢዎች ለማለት በሚያስደፍር መልኩ ህብረተሰቡ በመንግስት ላይ ያለውን ተቃውሞ እያሰማ ነው። መንግስትም በበኩሉ የፈሪ ዱላውን እያወረደው ይገኛል። እውነቱን ለመናገር መፍራት ተቃወሞ የሚያመጣ ተግባር ሲፈጽሙ ነበር እንጂ ተቃውሞውን አለነበረም።
Wallaggaa2014_3
ኢህአዴግዬ በክላሿ ተማምና ያላስቀየመችው የህብረተሰብ ክፍል ካለ እርሱ ኢህአዴግን እንደ ግል አዳኙ የተቀበለ ብቻ ነው። ዛሬ በኦሮሚያ ክልል ሰላማዊ ተቃዋሚዎች ላየ እየተወሰደ ያለው ርምጃ በተመሳሳይ መልኩ በአማራ ክልል ጎንደርም እየተወሰደ ይገኛል ይሄው አይነት ከዚህ በፊት በጋምቤላ፣ በአዲሳባ፣ በደቡብ ብሄር በሄረሰቦች ክልል ሀዋሳ እና ተረጫ ወረዳ ላይ እንዲሁም በቅርብ ጊዜ በሀረሪ ከልል ሀረር ላይ ሲወሰድ ነበር። (እነዚህ በቀላሉ ያስታወስኳቸው ናቸው ማስታወሻ ብናገላብጥ ደግሞ ሌላም ሌላም ይገኛል)

በጥቅሉ እነደ ኢህአዴግ ያሉ ”ፋራ” አምባገነኖች ለሰላማዊ ተቃወሞ ሰላማዊ ምላሽ ሲሰጡ ታይቶም አይታወቅ። እኛ የምንጸለይ የነበረው ኢህአዴግ ገደላውን ትታ የምትጠየቀውን እንደ ዘመናዊ ገዢ ፓርቲ፤ በቅጡ ብትመልስ ነበር። ግን አልሆነም። በዚህም የተነሳ እስከ አሁንም ድረስ በኦሮሚያ ክልል ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰላማዊ ዜጎች በአልሞ ተኳሾች እና ሳያልሙ ተኳሾች ተገድለዋል ቆስለዋልም።

ይህ ህመም የኦሮሚያ ክልል ነዋሪዎች እና ዘመዶቻቸው ብቻ ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያውያን ነው። ሰለዚህም ሁሉም በያለበት እና በየ አቀሙ ጩኸቱን ሊቀባበል ይገባል የምለው።

“አንተ ውጪ ቁጭ ብለህ….”

ወጪ ሀገር የሚገኝ ሰው የሚገጠመው ትልቁ ፈተና ይሄኔ ነው። ጩኸቱ የጋራ ነው ብዬ ስናገር አንዳንድ ወዳጆች ገና አንብበው ሳይጨረሱት ሁላ “አንተ ውጪ ቁጭ ብለህ እኛን ልታስጭርስ” የሚል አስተያየት ለመጻፍ ሲያቆበቁቡ ይታየኛል። በተወሰነ ደረጃ እወነትም ውጪ ሃገር የሚገኝ ሰው “አይዟችሁ አትፍሩ በረቱ…” ብሎ ለማለት የሞራል የበላይነት እንደሌለው አምናለሁ።

ስለዚህም አትፍሩ ብዬ አልመክርም። ነገር ግን እየፈራንም ቢሆን፤ ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ ጩኸቱ የጋራችን እንደሆእነ ልናሳይ ይገባል፤ ይሄ ማለት የግድ አደባባይ ውጡ ብሎ ማደፋፍር አይደለም። ቢያንስ ግን ከገዳዮቹ ጋር ባለመተባበር ጩኸቱ እና ኡኡታው የእኛም መሆኑን ማሳየት እንችላለን ለማለት ነው።

በተጨማሪም በተለያዩ ሰለፎቻችን ላይ፤ ለምሳሌ ነገ በሚካሄደው የአንደነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ የእሪታ ቀን ሰላማዊ ሰልፍ ከሚያሰማቸው እሪታዎች አንዱ በኦሮሚያ እንዲሁም በአማራ ክልል ጎንደር ላይ እየተደረገ ያለውን የሰላማዊ ዜጎች ጭፈጨፋ የሚያወግዝ ሊሆን ይገባዋል የሚል እምነቴን ለማካፈልም ነው።

ከዚህ በተጨማሪም በጎንደርም ሆነ በኦሮሚያ አካባቢዎች እየተደረገ ያለውን ግድያ በሶሻል ሚዲያዎቻችን እና ባገኘነው አጋታሚ በማሰራጨት ጩኸቱ የጋራችን መሆኑን እናሳይ ለማለትም ነው። ምክንያቱም አንድም ዛሬ በተለይ በኦሮሚያ ክልል እየደረሰ ያለው ትላንት ብብዙዎች ላይ ደርሷል፤ ነገም በእያንዳንዳችን እንደማይደርስ ዋስትና የለንምና ነው!

በመጨረሻም

ህይወታችውን ላጡ ነፍስ ይማርልን!
ለቆሰሉት ምሀረትን ይስጥልን!
የሚገድሉትንም ክላሻቸውን ያክሽፍልን!

አሜን!

↧

ሰበር ዜና-ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉ ልዩ ምርመራ ተደረገበት

$
0
0
ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉ

ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉ

በካዛንቺስ አካባቢ የቅስቀሳ ስራ ይሰሩ የነበሩ አባላት የሚሰሩትን ለመዘገብ ከቀስቃሽ ቡድኑ ጋር የነበረው የፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ነብዩ ሐይሉ በታሰረበት የስድስተኛ ፖሊስ ጣብያ ከተያዘበትና በፍርድ ቤት ከቀረበበት ክስ ጋር በማይገናኝ ጉዳይ ሲቪል በለበሱ ደህንነቶች ምርመራ እንደተደረገበት ምንጮቻችን ጠቆሙ፡፡
የአዲስ አበባ መስተዳድር እውቅና ለሰጠው ሰላማዊ ሰልፍ የቅስቀሳ ስራ ለመስራት ወደ አራት ኪሎና ካዛንቺስ አቅንተው የነበሩት ሁለት የአንድነት አመራሮችና ጋዜጠኛ ነብዩ ሐይሉ ከትናንት ወዲያ ፍርድ ቤት ቀርበው የአስራ አንድ ቀን ቀጠሮ ተጠይቆባቸው ወደ ፖሊስ ጣብያው እንዲመለሱ መደረጋቸው ይታወቃል፡፡
ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን በያዘበት ጉዳይ ምርመራ ማድረግ የሚችል ቢሆንም ነብዩን የመረመሩት ሲቪል ለባሾች ከክሱ ጋር ባልተያያዘ መንገድ‹‹ጋዜጠኛ መሆንህን እናውቃለን፡፡ከዞን ዘጠኝ አባላት ጋር ያላችሁን ግኑኝነትም ደርሰንበታል፡፡አዲሱ የጋዜጠኞች ማህበር ከውጪ ድርጅቶች ጋር እንደሚሰራ እናውቃለን››በማለት ማስፈራሪያ አዘል ምርመራ እንዳደረጉበት ምንጮቻችን አጋልጠዋል፡፡

↧
↧

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

$
0
0

ከነገው የአንድነት ሰላማዊ ሰልፍ መፈክሮች የተወሰኑት
—–
አንድነት ቅጥር ግቢ ውስጥ ለነገው ሰላማዊ ሰልፍ ዝግጅት ተጧጡፏል፡፡አባላትና አመራሮች መፈክሮቹን ከማዘጋጀት ጀምሮ የተለያዩ ስራዎችን እየከወኑ ይገኛሉ፡፡ከተዘጋጁት መፈክሮች መካከል የተወሰኑትን አቅርበናል፡፡

1027

↧

የሰማያዊ ፓርቲ አባላት አንድነት የጠራውን የሰላማዊ ሰልፍ እንደሚቀላቀሉ አስታወቁ

$
0
0


ethiopia-blue-party-300x164በተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች ታስረው የሰነበቱትና ቀሪዎቹ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ዛሬ ባደረጉት ሳምንታዊ የወጣቶች የውይይት ፕሮግራም አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) የ‹‹እሪታ ቀን›› በሚል የጠራውን ሰልፍ በግንባር ቀደምነት በመቀላቀል ድምጻቸውን እንደሚያሰሙ አስታውቀዋል፡፡
ወጣቶቹ ሰልፉን እንደሚቀላቀሉ ያስታወቁት ‹‹ሰላማዊ ሰልፉ ውጤታማ እንዲሆን በምን መልኩ ልናግዝ እንችላለን?›› በሚል አጀንዳ በተወያዩበት ወቅት ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ከውህደት በዘለለ በሰላማዊ ሰልፍም ሆነ በሌሎች የትግል ስልቶች መተባበርና አብሮ መስራት እደግፋለሁ የሚል አቋም እንደሚያራምድ በተለያዩ ሚዲያዎች መግለጹ የሚታወቅ ሲሆን ወጣቶቹ በሰላማዊ ሰልፉ የሚያደርጉት ተሳትፎ ፓርቲው ለትብብር ያለውን አቋም ያሳያል ብለዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ለሰላማዊ ሰልፉ ድምቀት የሚያገለግሉ ሜጋ ፎኖች፣ ጥሩምባዎችና ሌሎችም ሰልፉን ለማድመቅ የሚያገለግሉ መሳሪያዎችን ይዘው እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

↧

ሰላማዊ ሰልፉ ተጀመረ በመኪኖች ላይ በተገጠሙ ማይክራፎኖች አማካኝነት አዘጋጆቹ መፈክሮችን በማሰማት ላይ ይገኛሉ

$
0
0

udj demo 0

ሰልፉ ጉዞ ገና አልተጀመረም። ከመገናኛ እና ከራት ኪሎ ወደ ቀበና የሚመጡ ዋና መንገዶች ፖሊሲ ዘግቶ፣ ህዝቡ አቋራጭ እየፈለገ ነው እየመጣ ያለው። ከተጠበቀዉ በላይ ሕዝብ በአንድነት አካባቢ መጥቷል። ሰልፉ ገና አልተጀመረም ግን ወደ አስልፋልቱ እየተሻገሩ ነው። ከትንሽ ጊዜ  በኋላ ስለፉ ይጀመራል። መፈክሮች እየተሰሙ ነው። የአመራር አባላቱ ንግግር አድርገው ሰልፉ ሰላማዊ እንደሆነ በመግልጽ የሰልፉን ስነ-ስርዓት እያሰረዱ ነው።

 

udj demo 00

udj demo 2 udj demo 1
udj demo 4

                                     አንድነት ጽ/ቤት አካባቢ

↧

አንድነት በአዲስ አበባ ዛሬ የጠራው ሰልፍ በሰላም ተጠናቀቀ (ፎቶዎች ይዘናል)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) አንድነት ፓርቲ በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ የጠራው ሰልፍ በብዙ ወከባዎች እና እንግልቶች ቢታጀብም በሰላም መጠናቀቁን ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች አመልክተዋል። “ሰልፉ እጅግ በጣም ደማቅና አስገራሚ ሰልፍ ነው !” ያሉት የዜና ምንጮቻችን “በጥይት በዱላ አይገዛም አገር፤ በጥፊ በርግጫ አይገዛም አገር፤ ፖልሲ የሕዝብ ነው !መብትን መጠየቅ ሽብር አይደለም፤ አትነሳም ወይ አትነሳም ይሄ ባንዲራ ያነታ አይደለም ወይ !ሕገ መንግስቱ ወረቀት ብቻ !” በማለት መንግስትን ሲያወግዙ ውለዋል። በተለይም ሰልፈኞቹ ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ተማሪዎች ላይ የደረሰውን ግድያም አውግዘዋል።

ከተሰሙት መፈክሮች መካከል፦

የፈሪ ዱላ ጀግና ማሰር ነው !

ልማት እያሉ ሙስና  ሰሩ !

ድል የህዝብ ነው !

 ድምጻችን ይሰማ !

 ዛሚ ሌባ!

ተማሪዎችን የገደሉና ያቆሰሉ ለፍርድ ይቅረቡ !

ስድስቱ ጦማሪዎችና ጋዜጠኞች ይፈቱ !

 መግደል ይቁም !

እየገደሉ ገደሉ አሉ !

ራሱ ገዳይ ራሱ ከሳሽ !

ውሸት ሰለቸን ኢቴቪ ሌባ ህዝቡ በአንድነት ሰልፍ ካስደመጣቸው መፈክሮች ይመደባሉ :

መብትን መጠየቅ ሽብር አይደለም !

ውሃ ፣መብራት፣

ኔት ወርክ ፣ትራንስፖር !

ፍትህ እያሉ ቃሊቲ ገቡ !

ፍራቻው ይቅር ተቀላቀሉ !

ለፍትህ ብለው ቃሊት ገቡ ! በመግደል በማሰር አይገባም አገር !

ተከበረሽ የኖርሽው ባባቶቻችን ደም ፣ እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይዉደም ! እያለ ህዝቡ እየዘመረ ነው።  ሰልፉ ተጀምሯል።  መፈክሩ ደምቋል። እስክድነር፣ ርዮት ፣ አንድዋለም …እያሉ የሕሊና እስረኞቹን እየጠሩ ነው። «አሸባሪ አይደለንም !» እያሉ ነው።

«ኢትዮጵያ ካድሬዎች እንደፈለጉ የሚፈነጩባት አገር አትሂንም»፣ « አንድ ሕዝብ ነን።  በቋን ቋ፣  በባህል፣ በሃይማኖት ሊከፋፍሉን ሞከር። አልተሳካም»   …የመሳሰሉ መፈክሮች እየተሰሙ ነው።

udj-demo-18

addisdemo3

addis_demo 1

udj demo 3 udj demo 15 udj demo 8 udj demo 7 udj demo 9 udj demo 2


udj demo 9


udj demo 00

udj demo 6

udj demo 12 udj demo 11
udj demo 13

udj demo 14

udj demo 18 udj demo 16 udj demo 17

↧
↧

ዘረኛው እና አምባገነኑ የትግራይ ነጻ አውጪ ስርኣት በአገራችን ኢትዮጵያ እያደረሰ ያለዉን በደል ለመቃዎም የተጠራ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በዋሽንግቶን ዲሲ

$
0
0
↧

መኢአድ መግለጫ አወጣ፤ በሳውላ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ

$
0
0

aeup
ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የተላለፈ ጋዜጣዊ መግለጫ

“ሕዝባዊ አንድነት ለነፃነት”

ለአለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት የሕዝብን መብት በመቀማትና አፍኖ በሥልጣን ላይ የሚገኘው የህወሃት/የኢህአዴግ መንግሥት ዜጐች በአገራቸው ውስጥ በመዘዋወር ሰርተው እንዳይኖሩ ያገደ ብቻ ሳይሆን በተወለዱበትና እየኖሩበት በአለው ቀያቸውም የገዠው ፓርቲ አባል ካልሆኑ ወይም ደግፈው ካልቆሙ ይሰደዳሉ፣ ይበታሰራሉ፣ ይደበደባሉ፤ በተለያዩ ምክንያቶችም ንብረታቸውን ይቀማሉ፡፡

የተቀዋሚ ፖለቲካ ድርጅት አባል ከሆነ ደግሞ ጫናው ምን ያህል እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ በዚሁ መመሪያቸው መሠረትም በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ የመኢአድ አባላትና ደጋፊዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየተፈጸመባቸው ይገኛል፡፡ ከሰብአዊ መብት ጥሰቶች መካከልም ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህልም፡-

1. በደቡብ ክልል በሰሜንአሪ ወረዳ በጉዛ ዚፍቲ ቀበሌያት የሚኖር ሕዝብ ሕገ-መንግሥታዊ መብቻውን ተጠቅመው በመኢአድ ጥላ ሥር ስለተደራጀና ጽ/ቤት ስለከፈቱ ብቻ ሦስት (3) አመራሮቻቸው በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ ፍትህም ተከልክለው ሰሚ አካል ሊያገኙም አልቻሉም፡፡

2. በጐፋ ልዩ ዞን የሚገኙ የመኢአድ አመራሮችና አባላት ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸውን ተጠቅመው ስለተደራጁ ብቻ ከፍተኛ ድብደባና እስር ደርሶባቸዋል፤ የፓርቲው መታወቂያቸውንም እንዲነጠቁ ተደርጓል፡፡ በአሁኑ ጊዜም አስራ ሁለት (12) የመኢአድ አባላት በሳውላ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡

3. በደቡብ ክልል በደራሼ ልዩ ወረዳ የመኢአድ የወጣቶች የአመራር አባል በጩቤ ተወግተው ለፍትህ አካላት አቤት ቢሉም መልስ አጥተው በችግር ላይ ይገኛሉ፡፡

4. በአማራ ክልላዊ መንግስት በአንካሻ ወረዳ የሚገኙ የመኢአድ አመራር በኢህአዴግ ካድሬዎች ተደብድበው በሕክምና ላይ ይገኛሉ፡፡ ከትናንት በስቲያ ማለትም ሚያዚያ 22 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በጐንደር ከተማ በመንግሥት ታጣቂዎችና በሕዝቡ መካከል በተፈጠረው ግጭት ምክንያት የብዙ ዜጎች ሕይወት እንዲጠፋ ሆኗል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ብዙ ዜጎችም ከቤታቸው እየታፈኑ ወደ አልታወቀ ቦታ እንዲወሰዱ በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡

5. በተለያዩ ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች በመማር ላይ የሚገኙ ተማሪዎች ከመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ጋር በአደረጉት ግጭት ምክንያት ብዙ ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተው፤ ብዙ ንብረትም ወድሟል፡፡ ይህ የሚያሳየን የህወሃት/ኢህአዴግ መንግሥት የማስተዳደር ስልት ችግሩን በዘዴ በመፍታትና በማግባባት ሳይሆን ኃይልን በመጠቀም ላይ ብቻ ያተኮረ መሆኑን ነው፡፡ በአጠቃላይ እንደዚህ ያሉ የከፉ የሰብአዊ መብት ረገጣ አገር ተረካቢውን ወጣት ምሁር ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ አድርጓቸዋል፡፡

ስለዚህ የመላው ኢትዮጰያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን በመቃወምና ከተበዳዮች ጐን የቆመ መሆኑን ለማሳየት “ሕዝባዊ አንድነት ለነፃነት” በሚል መሪ መፈክር በመላ አገሪቱ ሕዝባዊ ንቅናቄ ለመፍጠር ከዜጎች ጐን የቆመ ድርጅት መሆኑን ለማሳየት ሰላማዊ ሰልፎችን አዘጋጅቷል፡፡ በዚሁ መሠረትም እሁድ ግንቦት 3 ቀን 2006 ዓ.ም በጐፋ ልዩ ዞን በሳውላ ከተማ ከፍተኛ ሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ አድርጓል፡፡

ስለዚህም የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለነፃነት ሲል ከጐናችን እንዲሰለፍ ታላቅ ሕዝባዊ ጥሪ ያስተላልፋል፡፡
አንዲት ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
ሚያዚያ 24 ቀን 2006 ዓ.

↧

(የሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ) ሁሉም ለበጎ ነው

$
0
0

debereselam-medhanialem
በቀለ ገብርኤል (ሲሳይ) – ከሚኒሶታ

እስኪ ወደ ኋላ ሄድ ብለን ያለፍንበትን መንገድ በትዝታ እንቃኝ – ጥናታዊ ጹሑፍ በሁለቱም ወገን ይቅረብ ተብሎ ለወራት ከተዘጋጁ በኋላ፣ የቀረበውን ካዳመጥንና ከሰማን በኋላ ስድስት ሰዓት የፈጀው ስብሰባችንን ማንም ሰው ረግጦ ሳይወጣ ድምጽ ቢሰጥበትም ኮረም አልሞላም በሚል ወዝግብ ተነስቶ አሁን ላለንበት ደረጃ ደርሰናል። ፍረድ ቤት ጣልቃ ገብቶ ይገላግለናል ያልነው፣ ምንም እንኳን ጠቅላላ ጉባሄ እንዳይጠራ ቢሞከርም፣ ነገር ግን እኛው እንድንወስንበት ጉዳያችንን ተመልሶ ወደ እኛ መጥቷል።

ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

↧

ሐገራዊ ጥሪ በዌኔፒግ ካናዳ ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን

$
0
0

በካናዳ ዌኔፒግ ግዛትና አካባቢዋ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን የቀረበ ጥሪ። ኢትዮጵያን በዌኔፒግ ከፍ ለማድረግ የቀረበ ጥሪ፦
Winnipeg Canada

↧
↧

በደቡብ ኮሪያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወቅታዊ መግለጫ፡ ያምማል! አፍንጫን ሲመቱት ዓይን ያለቅሳልና!

$
0
0

6 killo University
እኛ የኦጋዴን፣ የኣማራ፣የኦሮሞ፣የትግራይና የደቡብ ብሄር ተወላጆች ኣዲስ ኣበባን ለማስፋፋት በሚል ሽፋን በኣዲስ ኣበባ ዙሪያ የሚገኙ ድሃ የኦሮሞና ሌሎች ገበሬዎችን ግፍ በጥብቅ የምናወግዝ ሲሆን በቅርቡ በሃረማያ፣ በኣምቦ እና በሌሎች ኣካባቢዎች የሚኖሩ የኦሮሞ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ላይ የኢትዮጵያ መንግስት የወሰደውን ግድያና በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን ሊገልጹ በወጡ ተማሪዎች ላይ እየተወሰደ ያለውን የድብደባና የማጉላላት ዘመቻ በጥብቅ እናወግዘዋለን። ገዳዮቹም የጊዜ ጉዳይ እንጂ በፍትህ ፊት ቀርበው የእጃቸውን እንደሚያገኙ ኣንጠራጠርም።

እኛ ኢትዮጵያዊያን ልብ ልንል የሚገባው ጉዳይ ባለፉት ዘመናት እንደታዘብነው የኢህዓዴግ መንግስት ሲያሻው ብሄር እየለየ ሲያሻው በጅምላ ሰላማዊና ለውጥ ፈላጊ ዜጎችን ሲያሰቃይ ሲገድል ቆይቱኣል። ኣንዴ ኦሮሞን፣ ኣንዴ ደቡብ ሲዳማን፣ ኣንዴ ኣማራን፣ ኣንዴ ኦጋዴንን፣ኣንዴ ጋምቤላን ወዘተ ሲያጠቃ ተላላ ሆነን የተጠቃው ቡድን ብቻ ለብቻው ትንሽ ጮሆ ዝም ስለሚል የግፉ ጊዜ ሊረዝምብን ችሏል። ኣሁን ግን የኢትዮጵያ ህዝብ የመንግስትን የከፋፍለህ ግዛው ዘዴ ሊነቃበትና ኣፍንጫን ሲመቱት ኣይን ያለቅሳል እንደሚባለው ኣንዱ ሲጠቃ ሌላውም ሆ! ብሎ በመነሳት ይህንን ኣስከፊና በዓለም የሌለ ብሄርተኛ ኣገዛዝ ኣሽቀንጥሮ መጣል ይገባዋል።በሌላ በኩል የኦሮሞ ወገኖቻችን ያነሱትን የፍትህ ጥያቄ ለማጣመምና ብሄርን ከብሄር ለማጋጨት የኢህዓዴግ ካድሬዎች ሊሯሯጡ እንደሚችሉ እየተገነዘብን ይህንን ጉዳይ የኦሮሞ ተማሪዎች ይስቱታል ብለን ኣናምንም። መንግስት በተለይ በኣሁኑ ሰዓት የቀለም ዓብዮት ሊነሳብኝ ይችላል የሚል ትልቅ ስጋት ስላለበት ህዝቡን በሃይማኖትና በብሄር በመከፋፈልና ከፍተኛ የሆኑ የፍትህና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች በጋራ እንዳይነሱ ስለሚፈልግ ብሄርተኝነትንና ጠባብነትን ለብሶ እንደለመደው እያጋጨ በስልጣን ለመቆየት መፍጨርጨሩ ኣይቀርምና በማናቸውም ተቃውሞዎቻችን ውስጥ ለወያኔ እድል ፈንታ መስጠት የለብንም።

በሌላ በኩል ለውጥ ለማምጣት የሚታገሉ ዴሞክራት የፖለቲካ ፓርቲዎችም ቢሆኑ ኣንድ ብሄር ተለይቶ ሲጠቃ ሁሉን
የማንቀሳቀስና ለጋራ ትግል ቆራጥ የጥሪ ደወል የማሰማት ሃላፊነት ኣለባቸው ብለን በጽናት እናምናለን።

የጀግናው ብእረኛ እስክንድር ነጋ ነገር፣ በቅርቡ ደግሞ ወደ ዘብጥ የወረዱት የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ጉዳይ እንቅልፍ የነሳን ጉዳይ ነው። እነዚህ ወጣት የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን በሰፊው እስር ቤት የሚገኘውን የኢትዮጵያን ህዝብ የነጻነት እጦት ኑሮ ተምሳሊት ኣድርገው ይንቀሳቀሱ የነበሩ ለጋ ወጣቶች ወደ እስር ቤት መውረዳቸው ከሰፊው እስር ቤት ወደ ጠባቡ መግባታቸውን ከማሳየቱም በላይ የታሰሩት ግለሰቦቹ ብቻ ሳይሆኑ ኣላማቸው በመሆኑ ሌላው የዞን ዘጠኝ እስረኛ የሆነው ኢትዮጵያዊ ሁሉ መንግስት የነጻነት ጥያቄውን ወደ ወህኒ መወርወሩን የሚያሳይ በመሆኑ ምን ያህል መንግስት በጭካኔ ስራው ሊቀጥል እንደ ወሰነ ያሳያል። በመሆኑም የነዚህ ወገኖች መታሰር፣ የፖለቲካው ምህዳር ምን ያህል እየጠበበ መምጣቱን፣ መንግስት ለህዝቡ ያለው ንቀት ጫፍ መርገጡን ያሳያል። በመሆኑም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በብሄርና በሃይማኖት ሳይከፋፈል የኦሮሞ ወገኖቻችንን ወቅታዊ ጥያቄና የጋዜጠኖቹን እስር ጉዳይ ወደ ኣጠቃላይ ፍትህና ዴሞክራሲ ጥያቄ ከፍ ኣርገን በያለንበት እንነሳ :: ዴሞክራሲና ፍትህ ሲሰፍን ጥያቄዎቻችን ሊፈቱ ይችላሉና ኢትዮጵያዊያን በጋራ ለለውጥ እንድንነሳ ወገናዊና ወንድማዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!
የማትከፋፈል ኢትዮጵያን ለትውልድ እናሳልፋለን!
በደቡብ ኮርያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ድምጽ

↧

‹‹ትንሹ›› ተስፋዓለም (ከጽዮን ግርማ)

$
0
0

በአነጋገሩ ቀጥተኛና በጠባዕዩ ገራገር ነው፡፡ ‹ጥርስ ያሳብራሉ› በሚባሉ ስብሰባዎች፣ በኃይለ ቃል በተሞሉ የኤዲቶሪያል ውይይቶችና ግምገማዎች ሳይቀር ስሜቱን ውጦ በተረጋጋ መንፈስና በለዘብታ ቃል መመላለስ ጸጋው ነው፡፡ በኤዲቶሪያል ጠረጴዛዎችና ዴስኮች ዙሪያ በሐሳብ ለመግባባት ከሚደረጉ ግብግቦች ውጭና ባሻገር ቂምና በቀል አያውቅም፡፡ በደሙ ውስጥ ከሚዘዋወረውና ራሱን ከሰጠለት የጋዜጠኝነት ሞያውና የጋዜጠኝነት መርሕ የተነሳ ሌላ ዓለም፣ ሌላ ጥቅም፣ ሌላ ኑሮ ያለም አይመስለው፡፡ ለእርሱ ኑሮው፣ ለእርሱ ዓለሙ ተጨባጭ መረጃን ከወገናዊነት በጸዳ መልኩ ለሕዝብ ማድረስ ነው – ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ፡፡
አሁን ተስፋዓለም በማኅበራዊ ደረ-ገፅ ላይ ‹‹ዞን 9›› በሚል መጠሪያ ገጽ ከፍተው በመጦመር ከሚታወቁ ስድስት ጦማርያንና (Bloggers) ኹለት ጋዜጠኞች ጋራ በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማዕከል (ማዕከላዊ) ከታሰረ ዛሬ ዘጠኝ ቀን ኾኖታል፡፡ ተስፋለምን ጨምሮ ዘጠኙ ተጠርጣሪዎች የታሠሩት፤[ራሱን የመብት ተሟገች ነኝ ብሎ ከሚጠራ የውጭ ድርጅቶች ጋራ በሐሳብና በገንዘብ በመረዳዳት ማኅበራዊ ድረገፆችን በመጠቀም ሕዝቡን ለአመፅ ለማነሳሳት የተለያዩ ቀስቃሽ መጣጥፎችን ለማሰራጨት ሲዘጋጁ ተደርሶባቸዋል፡፡] በሚል እንደኾነ ፍርድ ቤት የቀረቡበት የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ ያስረዳል፡፡
tesfalrm
ተጠርጣሪዎቹ በጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር የዋሉት አርብ ሚያዚያ 17 ቀን ማምሻውንና ቅዳሜ ሚያዚያ 18 ቀን ነው፡፡ እሁድ ሚያዝያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም. ፍርድ ቤት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ነበር፡፡ በመዝገብ ቁጥር 118722 የቀረቡት የ‹‹ፎርቹን›› ጋዜጣና ‹‹የአዲስ ስታንዳርድ›› መጽሔት ፍሪላንስ ዘጋቢ ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ፣የአዲስ ጉዳይ መጽሔት ከፍተኛ አዘጋጅ ከአስማማው ኃይለ ጊዮርጊስና በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምሕርና የዞን ዘጠኝ ጦማሪ ዘለዓለም ክብረት ለ29/08/2006 ተቀጥረዋል፡፡በመዝገብ ቁጥር 118721 የተካተቱት የአዲስ ዘመን ጋዜጠኛ የነበረችው ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ፣የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎቹ ናትናኤል ፈለቀና አጥናፉ ብርሃነ ሲሆኑ ለ29/08/2006 ተቀጥረዋል፡፡ እንዲሁም በመዝገብ ቁጥር 118720 ሦስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች አቤል ዋበላ፣ በፍቃዱ ኃይሉና ማኅሌት ፋንታሁን ለሚያዝያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል፡፡ የምርመራ መዝገቡን ያዩት ዳኛ፣ ተጠርጣሪዎቹ በቀጠሮው ዕለት ጧት አራት ሰዓት እንዲቀርቡ አዘዋል፡፡
ተስፋዓለም ተይዞ በተወሰደበት ዕለት ምሽት ድርጊቱን በአካል ተገኝቼ ተመልክቻለኹ፡፡ ጎረቤታሞች እንደመሆናችን የተስፋዓለም አንድ ትርፍ የቤት ቁልፍ በእኔ ቤት ይገኛል፡፡ እናም የቤቱ ቁልፍ በአጋጣሚ አንድ ሌላ ጓደኛችን ጋር ነበር፡፡ ባለፈው ዓርብ ሚያዚያ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ከሠላሳ ደቂቃ አካባቢ የቤቴ በር ተንኳኳ፡፡ በወቅቱ ሰዓቱ መሽቶ ስለነበር እኔም ኾነ ቤት ውስጥ የሚገኙት እኅቶቼ በጣም ደነገጥን፡፡ በሩን ከመክፈቴ በፊትም ያንኳኳውን ሰው ማንነት ጠየቅኹ፡፡
ማንነቴን በስም ከጠራ በኋላ እንድከፍት አዘዘኝ፡፡ በድጋሚ ማንነቱን ጠየቅኹ፡፡ የተስፋዓለምን ስም ሲጠራ ደነገጥኹና ተንደርድሬ ከፈትኹ፤ ምክንያቱም እንዲህ ያለ ጥሪ አጋጥሞኝ ስለማያውቅ ችግር ገጥሞት ሊሆን ይችላል ብዬ ጠረጠርኹ፡፡ ተደናብሬ ስወጣ ፊቱ በቁጣ የሚንቀለቀል ወጣት ተስፋዓለም ስለተያዘ እንደምፈለግና ወርጄ እንዳናግር አዘዘኝ፡፡ እየሔድን መረጋጋት ስላቃተኝ ማንነቱንና የተፈጠረውን ነገር እንዲነግረኝ ጠየቅኹት፡፡ ‹‹ማንነቴ ምን ያደርግልሻል፤ እርሱን በኋላ ታውቂዋለሽ፤ አኹን ወደ ተጠራሽበት ሒጂ፤›› አለኝ፡፡
ቅርብ ለቅርብ ስለነበርን ወዲያው ደረስን፡፡ ትንሹ ተስፋዓለም ከእርሱ በገዘፉ ወጣቶች ተከቦ ሜዳ ላይ ቆሟል፡፡ ከእግሩ ሥር በፌስታል የተቆጣጠሩ ነገሮች ተቀምጠዋል፡፡ ኹለቱ ፌስታሎች የሚለበሱ ነገሮች መኾናቸውን አስተውያለሁ፡፡ ኹኔታው በእጅጉ ግራ ስለገባኝ ምን እንደተፈጠረ መወትወት ጀመርኹ፡፡ የተፈጠረውን የሚነግሩኝ ሳይሆን የሚቆጡኝ ድምፆች በረቱ፡፡‹‹የሚነገርሽን አዳምጪ፤ አንድ ትርፍ የቤት ቁልፍ አንቺ ጋር አለ አይደል?›› አሉኝ፡፡ ቁልፉ እኔ ጋር እንዳለ ነገር ግን የሚገኘው ሌላ ጓደኛችን ጋር እንደሆነ ነግሬ እኔን ወደ አሳሰበኝ ጉዳይ ተመለስኹ፡፡
ተስፋዓለምን ለምንና የት እንደሚወስዱት ለማወቅ ጎተጎትኹ፡፡ ሁለት እጆቹን በደረበው ሹራብ ኪሱ ውስጥ ከቶ መካከላቸው የቆመው ተስፋዓለም የሚሔደው ማእከላዊ እንደኾነና ከሥራ ጉዳይ ጋር በተያያዘ መኾኑን እንደተነገረው ነገረኝ፡፡ ከያዙት ወጣቶች መካከል ጭንቀቴን የተረዳው አንዱ ይህንኑ ደግሞ ኹለት የፖሊስ ልብስ የለበሱትን ሰዎች አመጣና ‹‹የሚወሰደው ሕጋዊ ቦታ መኾኑን እነርሱን አይተሸ አረጋግጪ››፤ አለኝ፡፡ ቤቱ ቢከፈትና ንብረት ቢጠፋ ተጠያቂ መኾኔን ከማስጠንቀቂያ ጋር በመንገር ትንሹን ተስፋዓለምን ብዙ ኾነው ይዘውት ሔዱ፡፡

ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ ተወልዶ ያደገው አዲስ አበባ ከተማ ነው፡፡ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን አባይ ምንጭ እና ተስፋ ኮከብ በሚባሉ ትምህርት ቤቶች፣ የኹለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በ‹‹ከፍተኛ አራት›› አጠናቅቋል፡፡ አሁን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሥር የሚገኘው የቀድሞው ማስሚዲያ ማሠልጠኛ ኤጀንሲ የጋዜጠኝነት ትምህርቱን በመከታተል ላይ ሳለ ‹‹ሰብ ሰሃራን ኢንፎርመር›› የተባለ የእንግሊዘኛ ጋዜጣ ላይ በገጽ ሥራና ቅንብር ባለሞያነት ተቀጠረ፡፡
ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላም የመዝናኛ ዜናዎችን በማዘጋጀት የጋዜጠኝነት ሥራን በዚኹ ጋዜጣ ላይ መሥራት ጀመረ፡፡ ቀጥሎም ‹‹ፎርቹን›› በተባለው ሳምንታዊ እንግሊዘኛ ጋዜጣ ላይ ተቀጥሮ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው ዘገባዎችን መሥራት ጀመረ፡፡ የ‹‹ፎርቹን›› ጋዜጣ አደረጃጀትና ኤዲቶሪያሉ ጠንካራ ስለነበር የጋዜጠኝነት ችሎታውን ለማሳደግ በጋዜጣው ላይ የሠራባቸው ዓመታት አግዘውታል፡፡
ከ‹‹ፎርቹን›› በኋላ የቀድሞው የዩኒቲ ዩኒቨርስቲ ባለቤት የነበሩት ዶ/ር ፍሥሓ እሸቱ ባለቤትነት የሚዘጋጅ ደረጃውን የጠበቀና በዲዛይን ውበቱ ትኩረት ሳቢ የነበረውን ‹‹ማይ ፋሽን›› የተሰኘ እንግሊዘኛ መጽሔት ገጾች ዲዛይን ይሠራ የነበረው ተስፋዓለም ነበር፡፡ ከዚኹ መደበኛ ሥራው ጎን ለጎን የአሶሺየትድ ፕረስ የዜና ወኪል ረዳት በመኾን ለውጭ ሚዲያዎች መሥራት ጀመረ፡፡
‹‹ማይ ፋሽን›› መጽሔት ከተዘጋ በኋላ በከፍተኛ ደረጃ ተነባቢነት የነበረውን ‹‹አዲስ ነገር›› ጋዜጣ ከሞያ ጓደኞቹ ጋራ መሠረተ፤ የጋዜጣው የዜናና ማኅበራዊ ፊቸር ገጾች አርታዒም ነበር፤ በዚኹ ወቅትም በተባበሩት መንግሥታት ሥር ለሚገኘውና በሰብአዊ ጉዳዮች ላይ ዜናና ትንታኔ ለሚያቀርበው ዓለም አቀፉ ኢሪን (IRIN) የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ኾኖ ይሠራ ነበር፡፡
በመንግሥት ጫና ምክንያት የአዲስ ነገር ጋዜጣው ከመዘጋቱ አንድ ወር በፊት በኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ጋዜጠኞች (EEJA) ማኅበር በኩል በዩጋንዳ የአንድ ዓመት የሥራ ላይ ልምድ ልውውጥ ዕድል አግኝቶ ስለነበር ወደዚያው አመራ፡፡ በፕሮግራሙ አጋጣሚና ከልምድ ልውውጡ ጎን ለጎን በዩጋንዳ የተለያዩ ብዙኃን መገናኛዎችና ‹‹ሩድሜክ›› በተባለ ሚዲያ ላይ ለአንድ ዓመት በሞያው ሲሠራ ቆይቷል፡፡
በዩጋንዳ የነበረውን የአንድ ዓመት የልምድ ልውውጥ ፕሮግራም ካጠናቀቀ በኋላ ቆይታውን በማራዘም ‹‹ሐበሻዊ ቃና›› የተባለ መዝናኛ ላይ የሚያተኩር ባለቀለም የአማርኛ ጋዜጣ ማዘጋጀትና ማሳተም ጀመረ፡፡ ጋዜጣው በአቅም ማጣት ምክንያት እስከተዘጋበት ጊዜ ድረስ በዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ታንዛንያና ደቡብ ሱዳን ውስጥ ይሰራጭ ነበር፡፡
በመጨረሻም ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ የጋዜጠኝነት ሥራውን ፍሪላንስ ኾኖ በመቀጠል ለ‹‹አዲስ ፎርቹን›› እና ‹‹አዲስ ስታንዳርድ›› የእንግሊዘኛ ጋዜጣና መጽሔት መሥራት ጀመረ፡፡ ቢቢሲን (BBC) ጨምሮ ከተለያዩ የውጭ ሚዲያዎች ጋራም በፍሪላንሰርነት መሥራቱን ቀጠለ፡፡ ከወራት በፊት የ‹‹ቢቢሲ››ዋ ዜና በዳዊ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ጋራ በአዲስ አበባ ያደረገችውን ‹‹ሃርድ ቶክ›› የቴሌቭዥን ፕሮግራም በረዳትነት ያዘጋጀው ተስፋዓለም ነበር፡፡
ተስፋዓለም የሚሠራው ዘገባ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ብቻ የተገደበ አይደለም፡፡ የሶማልያ ቀውስ በተባባሰበትና የኢትዮጵያ ጦር በአልሸባብ ላይ በዘመተበት ወቅት ስፍራው ድረስ ተጉዞ ዘገባዎች አስነብቧል፡፡ በተለይ ለምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች ትኩረት የሚሰጥ ሲኾን የሰሜንና ደቡብ ሱዳን ጉዳይን በሚመለከት በቦታው ተገኝቶ በቅርብ እየተከታተለ በ‹‹ፎርቹን›› ጋዜጣ ላይ ዘገባዎቹን አቅርቧል፡፡ ተስፋዓለም የወቅቱ የአካባቢ ጥበቃ ጋዜጠኞች ማኅበር የቦርድ ሰብሳቢ ከመኾኑም በላይ የአፍሪካ ኅብረትና ሌሎች ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፍረንሶች ላይ በመካፈል ዘገባዎችን ሠርቷል፡፡
በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀስ ማንኛውም ጋዜጠኛ ከየትኛውም ዓለም አቀፍ የዜና ተቋም ጋራ ሲሠራ ለኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች አሳውቆ ፈቃድ ማግኘት ይጠበቅበታል፡፡ የየትኛውም ድርጅት የዜና ወኪል ይኹን ጥናት አድራጊ የውጭ ዜጋ ወደ ኢትዮጵያ ለሥራ ሲገባ ስብሰባው ወይ ጥናቱ የት እንደሚካሔድ፣ ማንን እንደሚያናግር አሳውቆ ፈቃድ ማግኘት አለበት፡፡ በዚህ አሠራር መሠረት ተስፋዓለም ከበርካታ ዓለም አቀፍ የዜና ወኪሎችና አጥኝዎች ጋራ የነበረው ቆይታ ከኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ዕውቅና ውጭ አልነበረም፡፡
ተስፋዓለም በዕድሜው ሠላሳ አንድ ዓመቱ ነው፡፡ በጋዜጠኝነት ሞያ ላለፉት ዐሥር ተከታታይ ዓመታት አገልግሏል፡፡ ሥራ ሲጀምር በጣም ትንሽ ስለነበር ‹‹ትንሹ ተስፋዓለም›› የሚል ቅጽል በጓደኞቹ ተሰጥቶታል፡፡ በልጅነት ገጽታው ታላላቆቹ፣ ታናናሾቹም ኾኑ የዕድሜ አቻዎቹ እንደ ወንድም ስለሚቆጥሩት ‹‹ትንሹ›› የሚለው ቅጽል እስከ አሁን የሚታወቅበት ነው፡፡
ተስፋዓለም ግን ከስያሜው በላይ በእጅጉ ልቆ በሞያው ትልቅ ኾኗል፡፡ በሞያው የረገጣቸው አባጣ ጎርባጣዎች አብስለውት በሳልና በካር አድርገውታል፡፡ አንባቢነቱ፣ ነገሮችን በትኩረትና በተለየ መንገድ መመልከቱ፣ የማይሰለች ጠያቂነቱ፣ ተግባቢነቱና ጋዜጠኝነቱ ሰብእናውን አግዝፈውታል፡፡ ኹለቱንም ወላጆቹን በትምህርት ቤት ሳለና ገና ሥራ በጀመረበት ወቅት በሞት በማጣቱ እርሱና በሥሩ ያለችውን እኅቱን አይዟችኹ የሚላቸው ሰው አልነበረም፡፡ እናም ተስፋዓለምን በወጣትነቱ ማለዳ የተሸከመው የቤተሰብ ሓላፊነት እንደ አለት አጠንክረውታል፡፡ ‹‹ትንሹ›› ተስፋዓለም ማኅበራዊ ሓላፊነቱን ከኋላ ተሸክሞ እውነተኛ ጋዜጠኝነትን ለመተግበር በአያሌው ተግቷል፡፡
ተስፋዓለም ከኢትዮጵያ ውጭ ለመኖር የሚያስችሉት በርካታ ዕድሎች አዘውትረው ከፊቱ ይመጣሉ፡፡ እርሱ የሚመርጠው ለጋዜጠኝነቱ እገዛ ሊያደርጉለት የሚችሉ አጫጭር ሥልጠናዎችን እየወሰደ ወደ ሀገሩ መመለስ ነው፡፡ አገር ውስጥ የሚሰጡ ሥልጠናዎችም ተስፋዓለምን አያልፉትም፡፡ ‹‹ከኢትዮጵያ ከወጣኹ ከሞያዬ እለያያለኹ›› የሚል ስጋት ስለሚያድርበት አገሩ ላይ ኾኖ ክፉውንም ደጉንም እየተጋራ፣ ለሞያው ሥነ ምግባር ራሱን አስገዝቶ በሀገሩ ቁጭ ብሎ ይሠራል፡፡
ለሥራው ጥራት፣ ተጨባጭነትና ሚዛናዊነት ሟች የኾነው ተስፋዓለም የሚጠቅመውን መረጃ ለማግኘት ማንኛውንም መሥዋትነት ስለሚከፍል ሠርቶ ከሚያተርፈው ደመወዙ ይልቅ መልሶ ለሥራው የሚያውለው ወጪ ይበልጣል፡፡ እርሱ ኹሌም የገንዘብ ድኻ ነው፡፡ ያጠለቀው ጫማ በላዩ አልቆ እስኪቀደድ ድረስ ራሱን ለሥራው አሳልፎ የሚሰጥ የሳንቲም ድቃቂ የጨርቅ ዕላቂ ድኻ ነው!! ለዚህ ጠባዕዩና አኗኗሩ ከልጅነት እስከ ዕውቀት የሚያውቁት በርካታ ጓደኞቹ በምስክርነት ሳይቆጠሩ ምስክርነታቸውን ሰጥተውለታል፡፡
የተስፋዓለም ጓደኝነት ስለማይቆረቁር ባልንጀርነቱ ለብዙዎች ነው፡፡ ጋዜጠኝነት ከሚሰጣቸው ዕድሎች ዋነኛው ሠርክ አዲስ ሰው መተዋወቅ ነው ብሎ ስለሚያምን ወዳጆቹ በርካታ ናቸው፡፡ ኹሉንም ጓደኞቹን እንደየባሕርያቸው እስከአሁን አብሮ አቆይቶአቸዋል፡፡ ሰው ያሻውን ያኽል እንኳ ቢያስከፋው እንደ መሬት ነገር ቻይ እንጂ መከፋትን፣ መበቀልንና መቀየምን አያውቅም፡፡
እኔና ተስፈዓለም የምንተዋወቀው ፎርቹን ጋዜጣ በሠራንበት ወቅት ነው፡፡ ለጋዜጠኝነት እጃችንን ካፍታታንበት ፎርቹን ጋዜጣ ጀምሮ እስከ አሁንም ድረስ የልብ ጓደኛሞች ነን፡፡ ካለፈው አንድ ዓመት ተኩል ጀምሮ ደግሞ ጎረቤታሞች ኾነናል፡፡ተስፋዓለም መረጃ ለማግኘት በሚያደርገው ጥረት ሁሌም አደንቀዋለኹ፡፡በኦሞ የተከሰተው ጎርፍ በኮረንጋት ደሴት የሚገኙትን ዳሰነችና ኛንጋቶም ቀበሌ ነዋሪዎች ጠራርጎ እየወሰዳቸው መኾኑን እንደሰማ በቦታው ተገኝቶ ዘገባውን ለመሥራት፤ጭነት በያዘ አይሱዙ መኪና ላይ ከጭነቱ ላይ ተቀምጦ ሌሊቱን በሙሉ በመጓዝ አርባ ምንጭ ገብቶ ያደረውን መቼም አልረሳውም፡፡
ተስፋዓለም የመታሰሩ ወሬ እንደተሰማ ስለተስፋዓለም አስተያየት የሰጡ ብዙዎች ናቸው፡፡ በተለይ በየፌስ ቡክ ገጾቻቸው እየወጡ ስለእርሱ “one of the prominent journalist” በሚል የመሰከሩለት የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ጋዜጠኞች ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡ የኹሉም አስተያየት ግን እርሱ ለጋዜጠኝነት ሞያው የሚሰጠው ክብርና ዋጋ ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡
የረጅም ጊዜ ጓደኛውና የቀድሞ የሥራ ባልደረባው ስመኝሽ የቆየ (ሊሊ) ‹‹ተስፋዓለምን የተዋወቅኹት ሥራ እንደጀምርኹ እርሱ ፎርቹን እኔ ደግሞ ሰብ ሰሃራን እየሠራሁ ነው፡፡ ገና ስቀጠር በጊዜው የሥራ ባልደረባዬ የነበረ ጋዜጠኛ እንዴት ጠንካራ ጋዜጠኛ መኾን እንዳለብኝ እየመከረኝ በየመሀል እንደ ትልቅ ምሳሌ ያደርግ የነበረው አንድ ሰው ተስፋዓለም የሚባል ፎርቹን የሚሠራ ጋዜጠኛ እያለ ነበር፡፡ ጽሑፎቹንም እንዳነብና እንዴት የተሟላ ዘገባ መጻፍ እንደምማር ይመክረኝ ነበር፡፡›› ትላለች፡፡
አያይዛም‹‹ከሳምንታት በኋላ ተስፋዓለምን ሳገኘው ከተባለው በላይ ለሞያው ያለውን ታታሪነት በተግባር አየኹት፡፡ በሥራው ላይ ምንም ነገር ጣልቃ እንዲገባበት አይፈቅድም፤ አካሉም፣ አእምሮውም ልቡም ለጋዜጠኝነት የተሰጠ ነው፡፡ ጓደኝነታችን ጠንክሮ ዐስር ዓመት ሲዘልቅም አንድም ቀን ገንዘብ ሳያጓጓው አብዛኛውን የሕይወቱን ክፍል ከሰጠለት ሞያ በሻገር የዋህነቱን፣ ቀጥተኛነቱን፣ ለሰው ደራሽነቱን እና ጠንካራነቱን እያየሁ አብረን ኖርን፡፡ ተስፋለም ለኔ ከሞያ ባልደረባ አልፎ ጓደኛና ወንድም ኾነኝ፡፡›› ብላለች- ለፋክት በሰጠችው አስተያየት፡፡
‹‹ለመጀመሪያ ጊዜ ይዤ የመጣሁትን ዜና እንዲያርምልኝ ሰጥቼው፤ ወደጀመርኩት የኢኮኖሚ ጽሑፍ ተመለስኩ። ነገር ግን አፍታም ሳይቆይ በንዴት እየቀዘፈ መጥቶ “አሁን በዚህ ሌሊት ይህ ዜና ተብሎ ይሠራል….›› አለኝ ተስፋዓለም ለሞያው የሚቆረቆር። አንዳች ስሕተት መስሎ የሚሰማውን ፊት ለፊት ከመናገር የማይቆጠብ ነው፡፡ያን ሌሊት በብዙ ጭቅጭቅና ንትርክ ዜናው ተሠርቶ ወጣ። አጋጣሚው ግን ልዩነታችን በጋዜጠኝነት ፍልስፍና ላይ እንደኾነ ቁልጭ አድርጎ ያሳየ ነበር። እርሱ “ሚዛናዊ” ብሎ የሚሟገትለት ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሥርዓት አንዳች የማያራምድ ይልቁንም ጋዜጠኝነትን አሽመድምዶ ልሳን የሚሸብብ መኾኑ ሊያግባባን አልቻለም። እኔ “balanced journalism is a zero-sum game in Ethiopia” ብዬ እሞግተዋለኹ፤ እርሱ በየትኛውም የመንግሥት ሥርዓት ቢኾን የጋዜጠኝነት ሕግጋት የማይጣሱ ደንቦች ናቸው ይላል። ይህን ደግሞ በሥራው ያሳያል፡፡ጋዜጠኝነትን ሕይወቱ ያደረገው ተስፋዓለም በምንም መልኩ ቢኾን ሞያው በትምህርት ቤት ያገኛቸውን የጋዜጠኝነት መርሖዎች እንዲቃረን አይፈልግም። ዜናዎች ሲያዘጋጅ “ሚዛናዊነት” የሚለው መርሕ አለመጣሱን ሲያረጋግጥ ብቻ ነው ወሬው የኅትመት ብርሃን የሚያየው።›› ሲል በፌስ ቡክ ገጹ ስለ ተስፋዓለም ያሰፈረው የቀድሞ የ‹‹አዲስ ነገር›› የሞያ አጋሩ ጋዜጠኛ ዘሪሁን ተስፋዬ ነው፡፡
ከተስፋዓለም ጋር አብሮት የሠራው የቀድሞ የ‹‹አዲስ ነገር›› ባልደረባ ዳኝነት መኮንን፣ ‹‹ኹሌም ስለጋዜጠኝነት አለባውያን፣ መሠረታውያን፣ ቀመርና ሥነ ምግባር አብዝቶ የሚጨነቅ ምናልባትም ብቸኛው ጓደኛችን ነው። ጋዜጠኝነት ማለት accuracy, balance, clarity, and neutrality ከኾነ የማውቀው አንድ ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ ነው። የዜና ዘለላ መቁጠር፣ የፊቸር አለላ ማሰባጠር ማን እንዳንተ ተስፍሽ! ዜናና ታሪክ ሲሠራ ቀዳሚና ፊተኛው፤ እስረኞችን ቃሊቲ ወርዶ በመጠየቅ ታታሪው ወንድሜ ጠያቂና ስንቅ አሳሪ ያብዛልኽ።›› ብሎታል፡፡
‹‹ተስፋዓለም የግል ፖለቲካዊ አመለካከቱ ከጋዜጠኝቱ ጋራ እንዳይጋጭበት የሚጠነቀቅ ወጣት ነው። ለጋዜጠኝነት ከፍ ያለ ክብርና ዋጋ ይሰጣል። አንዳንዴ እቀናበታለኹ። ስለሚዛናዊነት፣ ስለተገቢነትና ስለእውነተኛ ዘገባ አብዝቶ ይጨነቃል። ማንኛውም ዐይነት ዘገባ ከትክክለኛው ወንዝ ተቀድቶ እንዲፈስ ይመኛል፤ ያደርጋል፤ ይጓዛል። መጀመርያ ለሞያው ታማኝ መኾንን ያስቀድማል። ከተስፋዓለም ጋራ ሳወራ ከታናሽ ወንድሜ ጋራ የማወራ ነው የሚመስለኝ። ኢሕአዴግ እንደ ተስፋዓለም መሥመራቸውን ጠብቀው ለሚሠሩ ሰዎች የማይመለስ ይኾናል ብዬ አስቤ አላውቅም። አኹንም መታሰሩን ማመን እውነት አልመስልኽ ብሎኛል! የሚሰማኝ፣ እልኽ፣ ቁጭት፣ ተስፋ ቢስነትና ቁጣ ነው። እኔ እስከማውቀው ድረስ ተስፋዓለም የማንም ወገን አይደለም። ብቻውን በራሱ የቆመ ጋዜጠኛ ነው፣›› ያለው የቀድሞው የ‹‹አዲስ ነገር›› ጋዜጣ ባልደረባው ማስረሻ ማሞ ነው፡፡
ከጋዜጠኝነት ት/ቤት ጀምሮ እስከ አኹን ጓደኛው የኾነው ጋዜጠኛ ደረጀ ብርሃኑ÷ ‹‹ተስፋዓለም ከኹሉም ጋራ ለመግባባት የሚሞክር፣ በት/ቤት በነበረበት ወቅት ጋዜጠኛ ለመኾን ከፍተኛ ፍላጎት ስለነበረው ሥራ የጀመረው ከኹላችንም ቀድሞ ትምሕርቱን ሳይጨርስ ነበር፡፡ ተስፋዓለም ኹልጊዜም አብረውት ቢኾኑ የማይሰለች፣ ጓደኝነቱና ጨዋታው የሚናፈቅ፣ ስለ ጋዜጠኝነት መሠረታዊ ቀመርና ሥነ ምግባር ቢያወራ የማይታክተው ጋዜጠኛ ነው፤›› ብሎታል፡፡
በ‹‹ሰብ ሰሃራ››ና ‹‹ማይፋሽን›› በሠራበት ጊዜ አለቃው የነበረው ዓለማየሁ ሰይፈ ሥላሴ፣ ‹‹ተስፋለም በየዕለቱ ለመለወጥ የሚጥር ታታሪ ልጅ ነው፤ ፍጹም ሞያዊ ጋዜጠኝነት ለማምጣትና ሚዛናዊ የኾነ ዘገባ እንዲሠራ ለማድረግ የሚጣጣርና የሚተጋ ጋዜጠኛ ነው፤ ይህን የሚያደርገው ደግሞ ራሱ ብቻ ሳይኾን ሌሎችን በመጎትጎት ጭምር ነው፡፡ የጋዜጣና የመጽሔት ዲዛይኖች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ኾነው እንዲሠሩ ለማደረግ የሚጥር፣ ከሌሎች ልምድ የሚቀስምና የራሱን ልምድ ለማካፈል ወደኋላ የማይል ጠንካራ ጋዜጠኛ ነው፤›› ብሎታል፡፡
የእውነትም ‹‹ትንሹ›› ተስፋ ዓለም ይኸው ነው፡፡ ማኅበራዊና ግላዊ ችግሮቹን ተቋቁሞ ስለ ጋዜጠኝነት ማውራትና ጋዜጠኛ ኾኖ መኖር የማይሰለቸው የአማናዊ ጋዜጠኝነት ተስፋ – ተስፋ ዓለም!!

↧

ከወያኔ ኢህአዴግ የጣር በትር አገራችንን እና ሕዝባችንን እንታደግ

$
0
0

ባለፉት ፳፫ የስልጣን ዘመኑ እንዲሁም ከዚያም በፊት በ፲፯ የጫካ ዘመኑ ኢትዮጵያን ከካርታ፣ ህዝቧን ከምድረ ገፅ ለማጥፋት ወያኔ አርነት ትግራይ ያልፈነቀለው ድንጋይ ያላፈሰሰው ደም የለም።
በባዕዳን ሁለንተናዊ ድጋፍ በመታገዝና በአንቀልባ በመታዘል በተለያዩ የአገሪቱ አቅጣጫዎች በመገስገስ ላይ እያለ በተለያዩ ግዛት ያሉ ኢትዮጵያውያኖች የዚህን እኩይ ግስጋሴ ለመግታት አይከፍሉ መስዋእትነት ከፍለዋል፤ የጣሊያንን ወረራ ለመመከት በግንደ በረት በረሃ ለሃገራቸው ኢትዮጵያ ተጋድሎ እንዳደረጉት እንደ አባት እናቶቻቸው አያት ቅድመ አያቶቻቸው የዘመኑ የአምቦ ትንታግ ወጣቶች የዛሬ ፳፫ አመት በወርሃ ግንቦት ባደረጉት ተጋድሎ የገበሩት ህይወት ምንግዜም የጀግንነት ታሪካቸው በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ትልቅ ስፍራ ይሰጠዋል።
የብሄር ብሄረሰብ መብት አስከባሪ ከኔ በላይ ላሳር ባዩ ወያኔ በቴሌቪዥኑ በየቋንቋው ከማዘፈንና ከማስለቀስ ያለፈ እኩልነት ኢትዮጵያ ውስጥ ታፍኖ በመቀበሩ፤ የማንነትና ፍትሐዊ የመብት እኩልነትን በጠየቁ በአፋር፣በኦጋዴን፣በአማራ፣በኦሮሞ፣በደቡብ ወዘተ ወገኖቻችን ላይ በተለያዩ ጊዜያቶች የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም ስልጣኑንም መከታ በማድረግ የህዝብን ሃብት ለመዝረፍ የጭቁኖችን መሬት በመቀማት የሚያደርገውን ጭፍጨፋ መዘርዘር ይቻላል። እነሆ ከዚሁ ጋር የተያያዘ ያልጠግብ ባይነት መዘዙ ተመዞ ሰይፍ ሆኖ ሰሞኑን የአምቦ ተማሪዎችን አንገት ቀልቷል።
ለህዝብ መብት መከበር፣ ለፍትሕ፣ ለእኩልነት እና ለዲሞክራሲ መስፈን የኢትዮጵያ ተማሪዎች ባለፉት ፵ አመታት የከፈሉት መስዋዕትነት አልበቃ ብሎ የዛሬውንም ትውልድ ደም እያስገበረ ይገኛል። ግና ትግል ትግል ነውና ወላድ በድባብ ትሂድ ፀረ ወያኔው ትግል ሰሞኑን በአምቦ ተማሪዎች ተለኩሶ በጅማ፣ በድሬዳዋ ፣በአዲስ አበባ፣ ሃረማያ ወዘተ እየተቀጣጠለ ይገኛል።
ባለፉት ወራትም በባህር ዳር፣ በደሴ፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባ፣በአዋሳ፣በአፋር፣በጋምቤላ በተለያዩ የኢትዮጵያ ግዛቶች ህዝባዊ አመፁና ሰልፉ እየተንቦገቦገ ይገኛል።
እኛ በዋሽንግተንና አካባቢዋ የምንገኝ የጋራ ግብረሃይልም ህዝባችን እያካሄደ ያለውን ትግል እየደገፍን በአምቦ የኦሮሞ ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ጭፍጨፋ አምርረን እናወግዛለን።
ለዚህም ነው ደማችሁ ደማችን ነው የምንለው፤ በልማት ስም ዘር ማጥፋት ይቁም እያልን ይህንኑ ድምጽ ለአለም ለማሰማት የፊታችን እሮብ ሚያዝያ ፳፱, ፳፻፮ ከጠዋቱ ፫ ሰአት ቀጠሯችን በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ይሁን እንላለን።
ቀን፦ MAY 7, 2014
ሰአት፦ 9:00 AM
ቦታ፦ U.S State Department
2201 C St NW
Washington, DC. 20520

የዋሽንግተን ዲሲ የጋራ ግብረሃይል

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live




Latest Images