Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

“በሐረር ከተማ በደረሰው ቃጠሉ ከዛም የክልሉ ፖሊስ በንጹሃን ዜጎች ላይ ጉዳት ማድረሱን በቸልታ አንመለከተውም”–አንድነት

$
0
0

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

Harar City
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

በሐረር ክልል ሕዝብ ላይ የደረሰውን ከፍተኛ ጉዳት አንድነት በቸልታ አይመለከተውም

የካቲት 30 ቀን 20006 ዓ.ም በታሪካዊቷ የሐረር ከተማ በጀጎል ሸዋበር በደረሰው ቃጠሎ እና ከዚያም በኋላ የክልሉ ፖሊስ በወሰደው እርምጃ በዜጎች ላይ ጉዳት መድረሱ የፓርቲያችንን አመራሮች፣ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጪ ያሉ አባላትና ደጋፊዎችን በእጅጉ አሳዝኗል፡፡

ምንም እንኳን የቃጠሎው መንስኤ ተጣርቶ ይፋ ያልተደረገ ቢሆንም በጀጎል ሸዋ በር እየደረሰ ያለው ተደጋጋሚ ቃጠሎ ድንገቴ ነው ለማለት የሚያስደፍር አይደለም፡፡ በተለይም በየካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም የተነሳውን ቃጠሎ በተገቢ ፍጥነት ለመቆጣጠር የክልሉ መንግስት ፍላጎት ያልታየበት መሆኑ፤ ይልቁንም ግሬደር መኪና አስጠግቶ ቦታውን ለማፅዳት መሞከሩ አጠያያቂ ነው፡፡ የክልሉ መንግስት ቃጠሎውን ለመቆጣጠር ተገቢውን ሁሉ ባለማድረጉ የጉዳቱ ሰለባ የሆነው ህዝብ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖበት ክፉኛ እንደ ተማረረ በዚሁ ምክንያትም ቁጣ ተቀስቅሶ ፖሊስ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ጉዳት ማድረሱንም በክልሉ የሚገኙ የፓርቲያችን አመራሮች መረጃውን አድርሰውናል፡፡

በመሆኑም ፓርቲያችን የክልሉ መንግስት ትክክለኛው የቃጠሎ መንስኤ በአስቸኳይ ተጣርቶ ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግ፤ በማንኛውም ምክንያት ኃላፊነታቸውን በብቃት ያልተወጡ የመንግስት ኃላፊዎች በግልፅ ለተጠያቂነት እንዲቀርቡ፤ የክልሉ ፖሊስ በህዝቡ ላይ የወሰደው የኃይል እርምጃ በገለልተኛ አካል ተጣርቶ ይፋ እንዲደረግ፤ የክልሉ ፖሊስ በወሰደው የኃይል እርምጃ ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች ብዛትና የጉዳቱ መጠን በአስቸኳይ ለህዝብ ይፋ እንዲደረግ ተገቢ ህክምና እና ካሳ እንዲከፈላቸው፤ ይህንን የፈጸሙ አካላትም ለፍርድ እንዲቀርቡ በአጽንኦት እንጠይቃለን፡፡

በአንድነት ፓርቲ በኩል ይህንኑ በህዝብ ላይ የደረሰ ጉዳት ለማጣራትና ለመከታተል በስራ አስፈጻሚው አስቸኳይ ግብረ ኃይል ተቋቁሟል፡፡ ግብረ ኃይሉ ወደ ቦታው በማቅናት ጉዳዩን ካጣራ በኋላ የደረሰበትን መረጃ እና በፓርቲያችን የሚወስደውን ተጨማሪ አቋም በተመለከተ በቅርቡ ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር
መጋቢት 4 ቀን 2006 ዓ.ም


በሴቶች ሩጫ ላይ በመንግስት ላይ ተቃውሞ አሰምታችኋል የተባሉ 7 ሴቶች እና 3 ወንዶች ፍርድ ቤት ዋሉ

$
0
0


ከዳዊት ሰለሞን

በሴቶች ሩጫ ላይ በመንግስት ላይ ተቃውሞ አሰምታችኋል የተባሉ 7 ሴቶች እና 3 ወንዶች ፍርድ ቤት ቀረቡባሳለፍነው ሳምንት ታላቁ ሩጫ ባዘጋጀው የሴቶች ውድድር ላይ በመሳተፍ ተቃውሞ በማሰማታቸው ለእስር የተዳረጉት ሰባት ሴቶችና ተባባሪ ተደርገው የታሰሩ ሶስት ወንዶች ዛሬ በነበራቸው ቀጠሮ መሰረት ቀበና በሚገኘው ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር፡፡

ታሳሪዎቹ በአንድ ፖሊስ ጣብያ ውስጥ የከረሙ ቢሆንም ፖሊስ ወደ ፍርድ ቤቱ በመጀመሪያ ያመጣው ወንዶቹን ነበር፡፡ሴቶቹ ለሰዓታት ዘግይተው በሩጫው ወቅት ለብሰውት የነበረውን ባለ ሙሉ ቢጫ ቀለም ቲ ሸርት እንደለበሱ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡

ዳኛው ከተሰየሙ በኋላ ከሳሽን በመወከል የቀረቡ ሁለት ፖሊሶች ‹‹ምርመራችንን ባለማጠናቀቃችን ተጨማሪ የሰባት ቀን የምርመራ ግዜ ይፈቀድልን››በማለት ጠይቀዋል፡፡የተከሳሾች ጠበቃ(የጋዜጠኛ ርዕዮት ወላጅ አባት አቶ አለሙ ጎቤቦ) ፖሊስ ደምበኞቼን በእስር ለማቆየት ካለው ፍላጎት እንጂ ወንጀሉ ተፈጸመ የተባለው በአደባባይ በመሆኑ ተጨማሪ ምርመራ አያስፈልገውም ስለዚህ ደምበኞቼ ጉዳያቸውን በውጪ ሆነው እንዲከራከሩ ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸውን ያክብርልኝ››በማለት ተከራክረዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ የመናገር እድል እንዲሰጣቸው በመጠየቅ ሲፈቀድላቸው ‹‹ሲቪል የለበሱ ሰዎች እየመጡ በሌሊት ጭምር ከታሰሩበት ቤት እንዲወጡ በማድረግ እንገድላችኋለን፣ከአሸባሪዎች ጋር መስራታችሁን አቁማችሁ አብራችሁን ስሩ፣በመጥረጊያ አናትሽን ብልሽ የሚደርስልሽ አይኖርም››የሚሉ ማስፈራሪያዎችን እንዳደረሱባቸው በመግለጽ ዋስትና ይሰጠን ሲሉ አቤት ብለዋል፡፡

ፖሊሶቹ በተከሳሾች የቀረበው ሐሰት መሆኑን በመግለጽ ‹‹ሴቶቹ ለምሳሌ ወደዚህ ለመምጣት የቆዮት የለበሱትን ቲሸርት እንዲለውጡ ሲነገራቸው እምቢ በማለታቸው ነው፡፡ በመኪና ላይ ይጨፍሩ ነበር፡፡እስር ቤት ውስጥም ሌሎች እስረኞችን ያነሳሳሉ ››ብለዋል፡፡

ቲሸርቱ በፍርድ ቤት እንዳይለበስ ያልታገደ በመሆኑ መልበስ መብታቸው ነው ያሉት አቶ አለሙ ‹‹ደምበኞቼን ፖሊስ በፈለገው ጊዜ ሊያገኛቸው የሚችል በመሆኑ በእስር መቆየታቸው ተገቢ አይደለም››ብለዋል፡፡

የግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጡት ዳኛው ‹‹ፖሊስ የእስረኞቹን መብት ማክበር ግዴታው ነው ስለዚህ የተባለው ነገር እንዳይደገም በማለት የዋስትና መብታቸውን ሳይጠብቁ ለፖሊስ ተጨማሪ አራት ቀን በመፍቀድ ተጠርጣሪዎቹ ወደ ፖሊስ ጣብያ እንዲመለሱ አዘዋል፡፡

[ዴሞክራሲያ ቅጽ 39 ቁ. 4 የካቲት 2006 ዓ.ም] –ለዳግማዊ የካቲት ሕዝባዊ አመፅ እንነሳ

$
0
0

eprp rt
የየካቲት 66 አብዮታዊ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ጉልህና ደማቅ ሚና ያለው ክስተት ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዝንተ ዓለም የሚያስበው የሚዘክረው ኹነት ነው። የአገዛዞች ጭቆናና ብዝበዛ መጠን እጅግ አድጎ ዜጎች መኖር የማይችሉበት ሁኔታ ሲከሰት የሕዝብን ቁጣና ብሶት ያዘለ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ሊፈነዳ እንደሚችል የሕብረተሰብ ሕግ ይደነግጋል። በዓለም ላይ አስከፊ አገዛዞችን ያርበደበዱና ከሥልጣን ያስወገዱ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች በጣም በርካታ በመሆናቸው ዝርዝሩን ማቅርብ አስቸጋሪ ቢሆንም በ19ኛውና በሃያኛው ክፍለ ዘመን የተከሰቱትን የፈረንሳዩንና የሩሲያ አብዮቶች፤ በ1989-90 ዓም በምስራቅ አውሮፓ አምባገነን አገዛዞች ያስወገዱትን ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንዲሁም በ2010-12 የአረብ የጸደይ እንቃስቃሴ የሚል ስያሜ የተሰጣቸውና በተለያዩ የአረብ አገሮች ተቀጣጥለው አምባገነን አገዛዞችን ያስወገዱትን ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ለአብነት መጥቀስ ይቻላል። በአገራችን በየካቲት 66 የተከሰተው አብዮታዊ እንቅስቃሴ በዓለም ውስጥ ከነበሩት አብዮቶች የተለየ ባይሆንም በወቅቱ ለ50 ዓመታት ያህል ስር ሰዶ የነበረውንና ማንም ሊያነቃንቀው የማይችልና መለኮታዊ ኃይል ነው ተብሎ ሲፈራ የነበረውን የአጼውን ሥርዓት ገዝግዞና አዳክሞ ከሥልጣን እንዲወገድ በማድረጉ በኢትዮጵያ
ታሪክ ውስጥ አቢይ ምዕራፍ ይዞ ይኖራል።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

[የለንደኗ ጽዮን ማርያም ቤ/ክ ጉዳይ] –ትግላችን ከሕወአትና ከግብረ-ዐበሮቹ ጋር ነው!

$
0
0

New Picture (15)
ፍርድ የእግዚአብሔር ነው! ወገን ተባበረን!
መጋቢት ፪ ፦ ፪ሺህ ፮ ዓም ከኮማንደር አሰፋ ሰይፉ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ።
ጻ! መንፈስ ርኩስ!!!
አሜን!!!
የቤተ ክርስቲያናችን ችግር ከጀመረ ረጅም ጊዜ ነው። አበው “ቁጭ ብለን የሰቀልነውን ቆመን ማውረድ አቃተን!” እንዳሉት ኾኖ ተካርሮ ለመዘጋት ከበቃች መጋቢት ፩ አንድ ዓመቱ ነው። ብዙዎቻችሁ ችግራችንን ችግራችሁ አድርጋችሁ ስትከታተሉ ስለነበር ሃተታ አላበዛባችሁም።
ባጭሩ፦ የመተዳደሪያ ደንባችን እንዲሻሻል ይወሰናል፦ከካህናትና ከምእመናን
አርቃቂዎች ይመረጣሉ፦በኅብረት ሥራቸውን ያኪያሂዳሉ
የልዩነታቸው መነሻ፦
መሠረቱ- የምእመናን ወኪሎች ቤተክርስቲያኗ ሕጋዊ ሰውነት እንዲኖራት
ያስፈልጋል ይላሉ።እስከዛሬ የተዳደርንበት ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀስ
ሃብትና ንብረትዋን በሚገባ አያስከብርላትምና። ይህም ማለት ባለዐደራዎቹን
በድምጽ ብልጫ ሕንፃ ቤ.ክርስቲያኗን ሳይቀር ለሌላ ሊያሳልፉ ያስችላቸዋል (አኹን በተጨበረበረ ሕጋዊነት፦ ምልአት እንኳን ሳይኖራቸው እንዳደረጉት) “ሊሚትድ ካምፓኒ ባይ ጋራንቲ” የሚባለው ግን ያለ ጠቅላላው ጉባኤ
ስምምነት በሃብቷና በንብረትዋ እንዳሻ ማዘዝ አይቻልም። ሲባል የካህናት ወገኖች ቀንዳቸው ቆመ። አለቃው ግን- ተስማምተው፦
- የሰበካ ጉባኤው ሊ. መንበር መነኩሴ እንዲኾን ፦
- አለቃውም፦- ደሞዝ ለመጨመር ፦
– ጉርሻ ለመስጠት
- የየንዑስ ኮሚቴዎች ሊ. መንበር እንዲኾን
ረቂቁ ውስጥ እንዲካተትላቸው ሲጠይቁ፦

ምእመናን አርቃቂዎች
ሊ. መንበሩ መነኩሴ ይኹን ማለቱ ቃለ- ዓዋዲውን “ከካህናት ውስጥ ይመረጣል” ስለሚል ያፈርሰውዋል። ያገሪቱንም ሕግ ይጻረራል፦ እንዲሁም የዴሞክራሲን መንፈስ፦ የተመዘገብንበትም የግብረሠናይ ድርጅት መመሪያ ስለሚንድ ልንስማማ አንችልም።
- ደሞዝ መጨመሩም የጠቅላላ የሰበካ አመራሩ ሥልጣን ስለኾነ፡
- ጉርሻ የተለመደ ስላልኾነና፡ ካስፈለገ ጉባኤው ሊወስነው ስለሚገባ
- የአለቃው የየንኡስ ኮሚቲዎችም ሊ. መ. መኾን፦ የየኮሚቴዎችን ሥልጣንና መብት ስለሚጋፋና ሥራ ስለሚበደል ፦
- አለቃው፦ በሊ.መንበርነት ሰበካ ጉባኤው ላይ የኹሉንም ከአባላቱ ጋር ኾነው ስለሚያዩት በገለልተኛ ዳኝነት ጉዳዩን ሊመረመሩት ይችላሉ። አለዚያ ግን ማንኛውንም በንኡስ ኮሚቴዎች የሚቀርበውን ኹሉ በፈለጉት መርተው ሰበካ ጉባኤው ስብሰባ ላይ ዳኛ በመኾን ፈንታ ጠበቃ በመኾን ሥራ ይበደላል፤፡ ስለዚህ
ንኡስ ኮሚቴዎችን ማጨናነቅና ሥራን መበደል ስለሚኾን
አንስማማም፦ በመባላቸው ካህናት ዐውደ-ምሕረቱ ላይ አሳዛኝና
አሳፋሪ ስብከታቸውን ቀጠሉ። ለአብነት አንድ ላቅርብ፦ “እኛ
ካህናት የምንለውን የማይቀበል በመንግሥተ-ሰማያት ቦታ የለውም።”

ይህ አባባል የቫቲካኖቹ የቅ. ጳውሎስን ርዕሰ አድባራት ሲሠሩና ገንዘብ ሲያጥራቸው ማይምኑን አማኝ፡”የሞተብህን ዘመድ እያሰብህ(ሽ) ገንዘብ ብትሰጠን የሞተብህ ዘመድ ከሲኦልም ቢኾን መንገሥተ-ሰማያት በቀጥታ ይገባል።” እንዳሉት አይደለም??!የኛዎቹ ግን ይባስ ብለው ወደራስ አዞሩት!!! አንዳንድ የታሪክ ጸሐፊዎች ስለዚህ ጉዳይ ሲጽፉ “ለማርቲን ሉተር የመጨረሻዋ ገለባ ይኽች ነበረች።”* ይላሉ። ጠንቁም ካቶሊክ ቤ.ክርስቲያንን አፍርሶ ፕሮቴስታንትን ወለደ። እኛ ጋ ምን በመፈለግ ነው??
የምእመናን አርቃቂዎች ጥያቄ አንድ ብቻ ነበር ነውም። ይኸውም ያረቀቅነውን የተማስማንበትንና ያልተማማንበትን ይዘን ወደ ሰየመን አካል (ጠ. ጉባኤ.) አቅርበን ጉባኤው ይወስን ቢሉ አሻፈረኝ ከማለት አልፈው – “የግል ኩባንያ ሊያደርጓት ነው..ለግላቸው ሊበደሩባት ነው… ምሥጢራት እንዲደፈሩ ሊያደርጉ ነው… ቀኖናን ያፋልሳሉ — ቃለ-ዓዋዲን ያፈርሳሉ ወዘተ” የወሬ ዘመቻ ባርቃቂ ጓደኞቻቸው፡ በቤ/ክርስቲያ ነባርና ቅን አገልጋዮች ላይ ከፈቱባቸው።

ይህ የወሬ ዘመቻ ያሳዘናቸው ሽማግሌዎች በገዛ ራሳቸው ተነሳሽነት ሊያደራድሩ ቢፈልጉ መለሷቸው። ምእመናን በዚህ ተስፋ ሳይቆርጡ ኹለት ጊዜ የተለያዩ ሽማግሌዎች የቀድሞው አለቃ “እኔን ካልደገፋችሁ በማለት አሳዝነውና አሳፍረው መርጠው ላኩ። የነእርሱም ልፋት ከመጀመሪያው አልተለየም። አሉባልታው ግን ነፈሰ።
እኔም፦ ‘እንዴት እንዲህ ይኾናል?’ በማለት ነበር ከምእመናን ዐርቃቂዎች አንዱን ስጠይቅ፦ በ ’እንዴት ጠረጠሩን’ ድምጸት የካህናቱ መግለጫ ባለፈው ሳምንት ነበር የኛ የሚቀጥለው ስለኾነ ሰምተው ይፍረዱ’ አለኝና ሄድሁ። ቀኖናውንና ቃለ-ዓዋዲውን ከካህናት በበለጠ አጥንተው፦ የፈረሰው በካህናት እንጂ በነርሱ አለመኾኑ ገልጸው “ እስቲ ቀኖና ፈረሰ ፦ ቃለ-ዓዋዲ ፈረሰ የምትሉትን በአንቀጽ ጠቅሳችሁ አቅርቡ ቢባል። ከየት??
ምእመናን አርቃቂዎች ለምእመኑ አንዲት የቀኖና አንቀጽ እንዳላፈረሱ፤- እንዲሁም ቃለ-ዓውዲውን ለሥራቸው እንደተመሩበት አስረዱ፤- ካህናት ግን ያወረዱባቸውን ሕዝቡን በሀሰት ሊያሳስቱ የሞከሩባቸውን በማስረጃ ሊያቀርቡ እንደማይችሉ ሲያረጋግጡባቸው፦
“ጌታዋን የተማመነች በግ ላቷን ከአጥር ወጪ ታሳድራለች።” እንዲሉ ‘መነኩሴ ናቸው፦ አደራ ያከብራሉ፦ ቤተክርስቲያናንን አክብረው ያስከብራሉ፦ እኛንም ያስተምራሉ፦ ብንጣላም ያስታርቁናል። ባህልን ጠብቀው ያስጠብቁናል፦’ ብሎ የመረጣቸውን ምእመን በአሳፋሪና በአሳዛኝ ኹናቴ ከድተው አገራችንንም ሃይማኖታችንንም ለታዛቢ ጣሏቸው።

እኔንና መሰል አዛውንትን የሚያሳዝነን ቅዱስ መጽሕፍና እምነታችን እጅግ ያልዘለቀላቸውን ወገኖቻችንን ስላሳሳቱብን ነው። ለሥልጣንና ሹመት ብሎም ለጥቅም መፈጽም ላይ ያሉትን ወንጀል፦ “ለሃይማኖቴ ነው ብሞትም ግድ የለኝ|!” ሲሉ በውኑ ለሃይማኖት መሞትን የሚፈልጉ ከኾነ፦ ከአንድ አምስት ስድስት ዓመት በፊት ሲኖዶስ ውስጥ ብዙ ካህናት በአክራሪ እስላሞች እንደሚገደሉ አቤቱታ ሲያቀርቡ፦ ሟቹ የሲኖዶስ ሊ.መንበር፦ እንደ መቼውም ልባቸው ሥራቸው ላይ ስላልነበረ ፡” ማሕበረ-ቅዱሳን ይላኩ፡” ቢሉ አንድ ልባቸው የተነካ የቤተክርስቲያኗ ልጅ በንዴት ተነስተው፦” አላሁ አክበር!” እያለ እጸድቃለሁ ብሎ ወደሚገድለው ማሕበረ-ቅዱሳን ይሂዱ ማለት ምንድር ነው?” ያሉትን በማስታወስ በዕውኑ ለሃይማኖታቸው ስማእትነትን ማግኘት ከፈለጉ የኛ የቀድሞው አለቃና ግብረ-ዐበር ካህናት ወዳሉበት ሠፈር ለምን አይሄዱም?” እዚህ ወጣቱንና ያልዘለቀውን ከማሳሳት? ማተባችሁን በጥሱ ያላችሁ አለ? ከኛ ወገንስ ማተቡን የበጠሰ አለ?
ሊ. ጳጳስ አባ እንጦስ እንዳሉት፤ ‘ቤትክርስቲያን መዝጋት መንፈሳዊ አይደለም።’ በኢመንፈሳዊነት አቢይ ጾም በተያዘበት ዕለት፡ ዘጓት!! ይህም ያለንበእትንም አገር የተመዘገብንበትንም ሕግ ይጥሳል። በማግሥቱ አንድ-ኹለት ካህናት ይዘው ወደ ኤምባሲ ዘለቁ። በሦሰትኛው ቀን ወደ ሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሊ.ጳጳስ ቢሄዱ፦ “ አንተ… ቀድሞውንስ እኛ እዚህ እያለን ኤምባሴ ምን ወሰደህ?” ተብለው ከተዘለፉ በኋላ በኹለቱ የገዥዎች ወኪሎች፦ በኤምባሲውና በጳጳሱ መካከል መመላለሱ ጦፈ።
እነሆ! ስደተኛ ነኝ፦ የአ.አበባውን ሲኖዶስ ለ.መንበር ስም በጸሎት አላነሳም፦ አቡነ እንጦስ የተባሉት የወያኔ ካድሬ እኔ ካልሞትሁ የማርያምን ቤ/ክን በር አይረግጧትም! ብለው የደነፉት ጠቅልለው ከገዥዎቹ ጉያ ገቡ። ገዥዎቹም፦ ምናቸው ሞኝ?! ‘እንዲህ ብለኸን/አርገኸን አልነበረም ሳይሉ እጃቸው እስቲገባላቸው ድረስ ያሽሞነሙኗቸዋል። ከቅ.ማርያም ወደ እነ ጳጳሱ የሄዱትን ኹሉ አግደዋል፤፡ በኋላም በዚህ ዓይነት ያባረሯቸውን ካህናት ጫማቸው ላይ ወድቀው ማሩኝ አሉ። በኛ ላይ ወገን ለማብዛት።
አዲስ አበባንም አዘወትሩ። ቶሎ ቶሎ እየተመላለሱ በሄዱ ቁጥር ደግሞ ሻንጣዎቻቸው እየተወጠሩ ነው። ‘በምን?’ ውስጥ የማንገባው ሳናውቀው ቀርተን ሳይኾን በትዝብት ማለፍን መርጠን ነው። አኹን ይህችን ጽሑፍ እንዳቀርብ ያስገደደኝ፦ በጥቅምትና ኅዳር በውጣው “ ዜና ቤተክርስቲያን ዘ ኢትዮጵያ ” ላይ የሰጡትን ቃለ-ምልልስ አይቼ ነው።
ለመመለስ ይህን ያህል ጊዜ የፈጀብኝ፦ለጽሑፌ ርዕስ ተቸግሬ ነው። እንኳንስ የመነኩሴ ቆብ የደፋውን ማንንም ‘ ዋሾ ‘ ማለት ይከብዳል። የባህል ተፅዕኖም ቀላል አይደለም። መተዉ ደሞ ሊላውን የማሳሳት ተባባሪ መኾን ነው። በዚህ ውስጥ እያለሁ መጀመሪያ የመጣልኝ ርዕስ

“ከእውነት ጋር የሚያስተዋውቅልን/ የሚያስታርቅልን ያለህ!” ነበር፦
“ከታማኝነትስ?”
የሚለው ደግሞ ይጠዘጥዘኝ ጀመር።
እያመነታሁ ሳለሁ ‘በፍኖተ ዴሞክራሲ’ የኢሓፓ ሬዲዮን ላይ በአንድ ወቅት
(ለኔ ጥሩ የዜና ምንጭ ያለው ኾኖ አግኝቼዋለሁ።

“ ለምን ይዋሻል? – እስከ መቼስ ይዋሻል?”

የሚለው ትዝ አለኝ። ይህን ወደ መምረጡ ላይ ሳለሁ በቅርቡ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ደግሞ፦

“ የምዋሸው ዕውነቴን ለመቆጠብ ብዬ ነው።”

የሚል ርዕስ አየሁ። አይጣጣ ! ምን እዳ ገባሁ? እያልሁ መጽሐፍ ቅዱሴን ለመግለጥ ሳስብ፦ ‘ በደረጃ ሂድ እንጂ! ‘ የሚል ስሜት አደረብኝ። ስለዚህ ስለ ‘ ውሸት ‘ ምድራውያን ዐዋቂዎች ምን ብለው ይኾን? በማለት ማገለባበጥ ጀመርሁ። እዚያም ላይ ወደ እምነት ተመሳሳዮቻን ሄድ ብዬ መቃኘትን ሳስብ፦ የሩሲያን ደራስያንን መረጥሁ። በዚያው ባነበብሁት ቋንቋ፦
london
Simply put by Leo Tolestoy,

“ Anything is better than lies & deceits.” ብሎአል

The writer of “ The Brothers Karamazov “ Fyrdor Dostoyevsky

“ Above all, don’t lie to yourself. The man who lies to himself and listens to his own lies comes to a point that he cannot distinguish the truth within him, or around him and so loses all respect for himself and for others and having no repsect he ceases to lose love.” (አጽንዖቱ የኔ)
ይህን የቀድሞው አለቃ በየሄዱበት ስብሰባም ኾነ ቀብር ወይም ድግስ ቀምሰውታል። (ለተመልካች እስከሚከብድ ድረስ) እኔም አልጠቅስም!

ታዲያ ምእመናን ወገኖቼ፦ የዶስቶየቪስኪው ምክር ቅዱስ ጳውሎስ በመጀመሪያው የቆሮንቶስ መልእክቱ ም. ፲፫ ላይ ልብ በሚሠብር ዓይነት ያሠፈረልንን አያስታውሳችሁም? በትንሹ እነሆ፦ አጭር ናትና ምዕራፏን ዝለቋት።አደራ !! አኹን ግን ከ ቁ ፩-፫ ያሉትን ላስነብባችሁ፤፡
“በሰዎችና በመላእክት ቋንቋ ብናገር ፍቅር ግን ከሊለኝ እንደሚጮህ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ኾኛለሁ።ትንቢት ቢኖረኝ፦ምስጢርንም ኹሉና ዕውቀትን ኹሉ ባውቅ፦ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ኹሉ ቢኖረኝ፦ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። ድሆችንም ልመግብ ያለኝን ኹሉ ባካፍል ፦ ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ፦ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም።”
ታዲያ በኛ ላይ የሚመጻደቁትና ልጆቻችንን ያሳቱብን ካህናት ምን ለማግኘት ነው? ከአካባቢያቸው ውርደትን፦ ንቀትን.. ለምን? በገዥዎች ለመሾም!?!?

ለሦስት ከፍለውን፦ አንዱ ወገን በሀዘን እቤቱ ሲቀር ፦ ሌሎቻችን በዚህ አገር መራር ብርድ በአቢይ ጾም ከገረገራው ስንጸልይ የኛ ካህን መላከ ብርሃን ብርሃኑ ወደዚያኛው ወገን በመሄድ “ እባክችሁ አብረን እንጸልይ። ተለያይተን የምንጸልየው አያርግም።” ብለው ቢማጸኑ ከነሱ መዘምራን አንድ-ኹለቱ “እኛ ከአሕዛብ ጋር አንጸልይም!” ሲሉ፦ ጥቂቶች ተጨመሩላቸው። እውን እነዚህ ልጆች የ”አሕዛብን” ስንኳንስ ትርጉሙን ቃሉን ዐውቀውት ነው?
ወንድም እህቶቼ ሆይ፦ ያስረዘምሁባችሁ ግንዛቤያችሁ የተሟላ እንዲኾን ነውና ይቅርታ። እንደምንም ብላችህ የመጨረሻዋን ገጽ ተመልከቱልኝ አደራ!

ጌታ በወንጌሉ ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ኹሉ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባህር መስጠም ይሻለው ነበር።” ማለቱ ተዘንግቶ ነው? ተንቆ!!
እዚህ ላይ ታናናሾቹ ሲል የእድሜ ጨቅላዎችን ብቻ አለመኾኑንእንደማይዘነጉት ተስፋ አለኝ።
በዜና ቤተክርስቲያን ላይ ለወጣው (የልብ-ወለድ) መግለጫ በብዛት ከላይ በተገለጸው የተሸፈነ ይመስለኛል፡፤ በተለይም ለችግሩ መነሻ የነበረውና አኹንም ድረስ ከቤተክርስቲያኗ ልጆች ጋር በጠቅላላ ጉባኤ ቀርቦ ከመነጋገር ብሎም ከመነጻጸር በየቦታው… የሚነዛው …ነው። አማርኛችን ሰፊ ሲኾን ለኹናቴው መግለጫ በሚኾኑት ለመጠቀም ትውፊትና ባህል ስለሚከለክሉ ልለፈው። የዜና ቤ/ክንን ለማጠቃለል፦ ከታሪክ መዝገብ
“ እባብ ሆነ ውቤ ሰውነቱን ትቶ
ሊነክ(ግ)ስ ነው አሉ ካቡን ተጠግቶ።”
የተባለውን “ያብዬን ለእምዬ!” ስለኾነ እዚያው ተቻቻሉበት። ከአቡኖች ብሎም ከሲኖዶስ የተጠጋው ማንነው? ያውም “ የፓትሪአርኩን ስም አልጠራም!” ካለ በኋላ!

አኹን በግለ ሰቦች ላይ በድፍንም ኾነ በነጠላ ሊያጎድፉ ስለሞከሩት ልመለስ።ከዜና ቤተ ክርስቲያን ሳልወጣ፦

“ ማንም ሳይወክላቸው ቤ/ክንን(ባልተጠቀሰ ቃለ-ዓዋዲ ተደግፈው)ኃላፊነቱ በተወሰነ የግል ኩባንያ ኹለት ግለሰቦች ባለንብረትነት በግል ስማቸውና በግል ባለ ንብረትነት በመኖሪያ ቤታቸው አድራሻቸው
በማስመዝገብ ቤ.ክንን በንግድ ተቋምነት ለመቆጣጠር እንዲያመች በሕገ ወጥ መንገድ በስውር አስመዝግበው፡ ተገኝተዋል።” ብለዋል። እግዜር ይቅር ይበልዎ።ድሮ የመስኮቡ ክሩሾቭ ሲናገሩ የሰማሁትን አስታወሱኝ። የቃል-በቃል ጥቅስ ሳይኾን መልእክቱ ‘ውሸትህ እንዲታመን ከፈለግህ እውነት ቀላቅልበት’ ነው። እዚች እጠቅስኋት ውስጥ እውነቱ ኹለት ጽኑ ስደተኞች ኢትዮጵያውያንና ለቤተክርስቲያንዋ በገንዘብም በጉልበትም የለፉ የተባለውን መፈጸማቸው ነው። ሌላው እውነት በግል ስማቸውና አድራሻቸው ማድረጋቸው ነው። ያደረጉበትም ምክንያት የቀድሞው አለቃ ለሌላ አሳልፈው ሊሰጡ ቢሞክሩ ባለቤት እንዳለው በማስመዝገብ በድብቅ ስም እንዳይዘዋወር ነው። ይህም ሠርቷል። የቀድሞው አለቃ ይህን ሊያውቁ የቻሉት የተፈራውን እኩይ ተግባር ሊፈጽሙ ሄደው ‘ ይህማ ባለቤት አለው!’ በመባላቸው አይደለም? እንግዲያውስ በባለቤትነት መመዝገባቸው እንዳለ ኾኖ ርሳቸውም በአለቃነቴ እንዳለሁ ነኝ እያሉ እያስቸገሩ ሳሉ፦ ታዲያ እነዚህ በባለቤትነት የተመዘገቡትን ግለ-ሰቦች በሕገ-ወጥነት ባለቤትነቱን ከወሰዱ ለምን አልከሰሱም? አለመክሰሳቸው ትልቅ የእምነት ጉድለትን አያሳይም? ሕጋዊ ተግባር መፈጸማቸውን ካወቁ ለምን ለአሉባልታ አበቁት? በሃሰት ለመወንጀል? ሊላው ሃተታ ኹሉ ክሩሾቭ እንዳሉት ነው።
-“ …ካህናት በሥርዐተ ጥምቀት ላይ በጸሎት እንዳሉ መስቀል በመቀማት…” እግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ! የማን መስቀል ተቀማ? ግቢውን በፖሊስችና በውድ ዋጋ (በኤምባሲ) በቀጠሯቸው በግል ጠባቂዎች ሞልተውት ነበር፦ ታዲያ እውነት ከነበረ የቢተክርስቲያኗ ንብረት ሲቀማ ለምን አላስመለሱም? ይህም
በሕግ የሚያስጠይቅ ነው።
የአንዳንድ ሰው ለልበ-ወለድ ነገር ያለው ስጦታ ይደንቃል።

“ …በሕገ-ወጥ መንገድ የመረጧቸውን ግለ-ሰቦች ስም ለባንክ በማስተላለፍ የቤተ ክርስቲያኑን የባንክ ሂሳብ በግለ ሰብ አድራሻ በማዞር …” እንዴ እስካሁን ድረስ እንዳሉት የቤተ ክርስቲያን ገንዘብ ሲዘረፍ እያወቁ ሕግ ባለበት አገር ዝም ካሉ ተጠያቂው ርስዎ መኽንዎን በራስዎ መሠከሩ። በችሎታ ማጣት ነው ይባል? ኃላፊነትን አለማክበር? ወይስ በግድ-የለሽነት?
- በተሰለጠነበት የልብ-ወለድ ዝባዝንኬ በኋላ “…ቤተ ክን ውስጥ በጫማቸው ዘልቀው በመግባት…” ፈሪሃ እግዚአብሔርን ፈጽማችሁ ከልባችሁ አውጥታችሁታል ማለት ነው? ይህ ኹሉ አገር ውስጥ ይህንን …የሚያነብቡትን የእምነት ወገኖቻችንን ለማሳዘን? ምን አጠፉ? እነርሱማ ሃዘን ምን ገድዶአቸው? በሽ-በሽ አይደለም እንዴ? ብሎም በኛ ለማስፈረድ? እንደተጫማ እንደ ኹል ጊዜም የሚገባ በእግዚአብሒር እጅ የተያዘና የአገሪቱም የጤና ተቅዋምተገቢውን ድጋፍ የሚያደርግለት አንድ ወንድማችን መኾኑን እያወቁ? አገር ውስጥ ያለውን ሕዝበ ክርስቲያንን ማሳሳት ይገባል? የውጪው አነሰና ነው?
እኛን ስደተኞችን ለማስጠላት? ይህ ወንድማችን ደግሞ የቤተ ክርስቲያኗ ጽኑ አገልጋይ መኾኑን የማያውቅ የለም።

ዜና ቤ/ክን አንድ ወገን ሰምቶ ሳያጣራ በዚህ ወገን ያለነውን ክብር በመንካትና ሌላውንም ሕዝብ በኛ ላይ በማሳሳቱ ይህን መልስ ለማስተካከያ ካላተመው በጸሐፊውና ባታሚው እንዲሁም በባለቤቱ ላይ ሕጋዊ ርምጃ የመውሰድ መብታችን የተጠበቀ መኾኑን እናስታውቃለን
“የጋዜጣው መለክት” ብሎ ውሸት ተቀብሎ ውሸትን ያባዛው በውሸትም አንባቢያን ወገኖቻችንን ያሳሳተው ሳይውል ሳያድር የሚገባውን ነገር መፈጸሙ ይጠቅመዋል። ይህ፦”ጌታዋን የተማመነች..” ሂደት ውሎ አድሮ ያስከፍላል።

ግለ-ሰቦችን በሚነካ ጉዳይ!

በገዜጣው ለወጣው የግለ-ሰቦችን ለማጠቃለል፦

“ ከካህናቱም መካከል እነ ቄስ ብርሃኑ ብሥራት የመሰሉት…” ተብሎ
የተጻፈው መላከ ብርሃን ብርሃኑ ናቸው? ሳይመነኩሱ የመነኩሴ
ባህርይ ያላቸው፦ የተማሩ፦የተከበሩና የተወደዱ፦ ጽኑ አገልጋይ
ጥሩ መምህር፦አርአያነታቸው የሚፈለግ፡ ናቸው ከሚኖሩበት ከለንደን
ከምስጋናና ፍቅር በስተቀር ስንኳን የጸያፍ ነቀፌታ ቅሬታ እንኳን ሰማሁ
ያለኝ አላጋጠመኝም። እስቲ ዘርዘር አድርጌ ግልጋሎታቸውን ለንባቢያን
ላቅርብ፦

ሀ- በአሜሪካ-
-ሜሪላንድ – ቦልቲሞር፦ ደብረ-ብርሃን ቅ. ሥላሴን መሥራች
-ላስቬጋስ – የኃመረ ኖኅ ኪዳነ-ምሕረት ወሚካኤል አቋቋሚ
ለ- በአውሮፓ፦
– ስዊድን፦ ደብረ-ሰላም ቅድስት ማርያም መሥራች
– ስዊትዘርላንድ፦በርን የደብረ-አሚን ተክለሃይማኖት “
– ሆላንድ፦ ዴንሃግ፦ የዉሉደ-ብርሃን የወጣቶች የሰንበት ት/ቤት መሥራች

ስለርሳቸው የሚሰማው ፍቅር፦ ውዳሴና አክብሮት ነው። ይበልጥ ደግሞ
ቀድሰው ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ፈትተው አቀብለው በመጨረሻ
በእጃቸው በሚያሳልሙበት ጊዜ ትንፋሻቸው ‘ቁርጥ-ቁርጥ’ እያለ፡ ወደ ሴቶች
ወተት ማውጫ ይወርዳል ተብሎ ተነግሮባቸው አይታወቅም።

ታዲያ እኒህን በስም ሳይመነኩሱ በግብር የመነኮሱትን በብቁ
ችሎታና በመልካም ግልጋሎታቸው ከቀድሞው አለቃ ቢያንስ
ከአራት ዓመታት በፊት
የ ‘ መልአከ ብርሃን ‘ ማእረግ የተሰጣቸውን በርስዎ የተነፈጋቸው በምን ሥልጣን ነው? ወይስ ማእረጉ የተሰጣቸው በብቸኛነት በአሜሪካ፦በዌስት ኢንዲስና በደቡባዊ አፍሪካ ለቤተ ክርስቲያናችን ከአርባ ሺህ
ልጆች በላይ ልጆች ባፈሩላት የምራባዊው ዓለም ሊቀ ጳጳስ በነበሩት መሾማቸው? ወይስ እኚህ የተቀደሱና የተባረኩ እውነተኛ የኢትዮጵያና የቤተክርስቲያኗ ልጅ ቆራጥ ልጅ በቀውጢው ጊዜ ልጅነታቸውን እንደ ብዙሐን ተብረክርከው ያልካዱ በስደተኝነት ለብዙሐን አርአያ መኾናቸው ተብረክራኪዎችን አስቀንቶ የርሳቸውን ሹመት ላለመቀበል የተደረገ ሴራ ነው? ጌታዬ ይግባኝ በሌለብት ቃሉ “ማንንም አባት አትበሉ!” ባይል እኒህን ሊ.ጳጳስ አቡነ ይስሐቅን ‘አባት!’ ብላቸው ክብር ይሰማኝ ነስበር። መሬት ይቅለላቸው።
ይህም ቢኾን፦ በቆሙበት አለመርጋት ነው። በአራተኛው ፓትሪአርክ የሚመራው የውጪው ሲኖዶስ የሾማቸውን እንቀበላለን ተብሎ የለ? አሳዛኝና አሳፋሪ! ይህ ኹሉ ልፋት ምድራዊ ጌቶቻችሁን ለማስደሰት? ታዲያ ጌታችን

’ለኹለት ጌታ…” ያለው ተፈጸመባችሁ አይደለም? ማንን ለማስደሰት?
ትርፉ ትዝብት ነው።
ወገኖቼ
“የገብርኤልን መገበሪያ የሰረቀ ሲለፈልፍ ያድራል!” ሲባል ሰምታችሁ የለ!?

“ይሁን እንጂ በለንደን ያለውየኢትዮጵያ ኤምባሲ በታቻለው መጠን እየረዳን ስለሆነ…”
ብለው አፍረጠረጡት፦ ይህ ተሰውሮን ሳይኾን… ሕገ-መንግሥታቸው
“መንግሥት በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ አይገባም።” ያለውን በማፍረጥረጥ ማስረጃ መስጠታቸውን ነው የወደድነው።

የኤምባሲው ርዳታ ምን ምንን እንደሚያጠቃልል በክፍል ኹለት እገልጻለሁ

እነዚህ በደርግ የጦር ሹማምንትነት የሚብጠለጠሉት የቀድሞው አለቃ “ከሸፈቱ ይቅርታ፦ እውነተኛ አቅዋማቸው ከተገለጸ በኋላ፦” የመጡ አይደሉም።ኹሉም፦ ማለት ይቻላል፦ከርሳቸው በፊት በተለያዩ የቤተክስቲያኗ ኮሚቴዎች ውስጥ ያገለገሉ ናቸው።ቤተክርስቲያኗም ከዕዳ ነጻ እስክትደርስም ኾነ በኋላ በተፈለጉበት ተግባራት ተሠማርተው አገልግለዋል አኹንም ያገለግላሉ። አንዳንዶቹማ መነኩሴ አገኘን ብለው እንደግል መኪና ነጅነት ድረስ ያገለገሉበት ወቅት ነበር። ዋጋቸው መወረፍ ኾነ እንጂ- በቀድሞው አለቃ በኩል!
ደግሞ ፖለቲከኞች – ፖለቲከኞች የሚባለው ባገር ላይ የተጫኑትን ተቃዋሚዎች ለማለት ነው እንጂ ሊላ ምክንያት ምንም የለ። ይህም ገዥዎቹ የሚቃወማቸውን ኹሉ “አሸባሪ!” እንዲሉ የገዥዎቹ ደጋፊነታቸውን ለማረጋገጥ የገዥዎቹን ተቃዋሚ ስደተኞችን “ፖለቲከኛ!” በማለት ለመቅረብ መኾኑን የሚያረጋግጥ ነው።
አንዱ ‘ፖለቲከኛ – ፖለቲከኛ’ ሲባል የመለሰው ለጥቅስ የሚገባ ነው። “እኔ እኮ ክርስቲያን የኾንኩት እንኳን ፖለቲከኛ ልባል ፖለቲካ የሚባል ነገር ሳልሰማ ነው።” አለ። የቀድሞውም አለቃ ፖሊስ ጠርተውና በዐውደ-ምህረቱ ላይ ከነጫማው እጁን ይዘው መጥተው ፖለቲከኛ የተባለው ወንድማችን ሲናገር፦ “ዚስ ዚስ ፖሊቲካ! “ ቢሉት ፖሊሱ ገርሞትና ታዝቦ “ እዚህ አገር ማንም ባመነበት የመናገር መብት አለው። ፀጥታ ያደፈረሰበት ኹናቴ የለም።” ብሎ እጁን አስለቅቆ እንደ ወጣ ተነግሮኛል። እዚህ ላይ በሰበባ-ሰበቡ ፖሊሶች ሲጠሩና ዐውደ ምሕረቱም ላይ ሲያንጓጓቸው ሳይጫሙ ኖሯል? ይህ ማነብነብ ከወጣትነት ትምሕርቴ አንድ ነገር አስታወሰኝ። “ብዙ ሲዋሹ ለአንዳንዱ ዕውነት ይመስላል”
የሚባለውን። ማንን ለማሳመንና ከማንስ ወገን ለመኾን የተደረገ ስልትና ጥረት እንደኾነ “ዶሮ ጭራ የምታወጣው ነው።”
በተረቀቀው ውስጥ አርቃቂዎቹ ‘ለፖለቲካ መነገገሪያ ትኾናለች’ የሚል እንኳን ተነባቢ ዐረፍተ-ነገር በአንድምታ የሚደረስበት ዐረፍተ-ነገር ቀርቶ መንፈሱ አለ??
ወደ ትውስታዬ ስመለስ ዝነኛው ሼክስፒር በጻፈው ጁሊየስ ሲዘር ላይ
“ ከንቱ ስባሄን አልወድድም!” ይላል ጁሊየስ ሲዘር፦ ጸሐፊውም
“እንዲህም በማለቱ ሲዘር ራሱን በከፍተኛ ደረጃ በከንቱ አወደሰ!” ይለዋል።(ከንቱ ስባሄ ለራሱ አደረገ ሲል ነው) የቀድሞውም አለቃ ፖለቲከኛነታቸውን በዚህ መልክ ያለማቋረጥ ያነበንቡታል።
አኹንም ወገኖቼ ሕወአትንና ግብረ-ዐበሮቻቸውን ለማስደሰት በተናገሩ ቁጥር የደርግ ከፍተኛ መኮንኖችንና በተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት ውስጥ ተሳታፊዎችን በመወረፍ ጌቶቻቸውን ሲያስደስቱ፦ሼክስፒር እንዳለው የራሳቸውን ፖለቲከኛነት በነጋሪት ያስተዋውቃሉ። ለማያውቃቸው!!!

ይባስ ብለው “ ንጉሡን ያወረዱ፦ ፓትሪአርኩን ያስገደሉ” ማለታቸው ተወርቶአል። እዚህ ላይ፤
“አንተ ግብዝ፦ ሌባ ጣትህን በሰው ላይ ስትቀስር ሦስቱ ጣቶችህ ወዳንተ ማመልከታቸውን አትርሳ” ያለውን ማስታስወስ ይጠቅማል። በ ፷፮ ዓም ወሬው ኹሉ ስለ ሶሺያሊዝም በነበረበት ጊዜና ሕዝቡም ስለሶሻሊዝም የሚያውቀው ፀር-ሃይማኖትነቱን ስለነበር ቆዝሞና አጉሞተሞቶ ነበር። ይሄን ጊዜ ያኹኑ ሊ.ጳጳስ መልከጼዴቅ፦ ሊ/ሥልጣናት ሃብተማርያም ለቤተክርስቲያናችን እሁድ እሁድ ጠዋት የሬዲዮ ፕሮግራም አስፈቅደውላት ስለነበር በዚች ፕሮግራም አንድ ጎረምሳ “ቀሲስ” ‘የሶሺያሊዝምና የወንጌል ትምሕርት አንድ ናቸው። ኹለቱም ኹለት ያለው አንዱን ለሌለው ይስጥ ይላሉ’ ብሎ ሕቡን ያስተኛ በማን ፈቃድ ነበር? ካለስ በኋላ ከቤ/ክን ሃላፊዎች “ወንጌልንና ሶሻሊዝምን በአንድ ዓይነት አታቀርብም!” ብሎ እንኳን ቅጣት ግሳጼስ አድርሶበታል? ሲኾንስ ጠንካራ ማስተባበያ መስጠት አይገባትም ነበር?? አኹን ታዲያ ‘የእምዬን ለአብዬ’ መስጠቱ ሕወ አትንና ግብረ-ዐበሮቹን በማስደሰት ለመሾም ነው?? ይበልጥ ደግሞ የስደተኛን ንብረት በማስረከብ!!! ማን ይኾን በነገ ሊያዝዝ የሚችል?

በጉዳያችን ገብተው ስለነበሩ ወይም ስለገቡ ሊ.ጳጳሳትና ስለ ሲኖዶስ በክፍል ኹለት እገልጻለሁ፡
አንዳንድ የቤት ክርስቲያኗ ልጆች፦በብዙ ልፋት አርቃቂዎች የሠሩትን ለባለ ጉዳዮች እንዲያቀርቡ ኾኖ፤- ካህናት የረቂቁን መግለጫ ተራቸውን ጨርሰው፦ የምእመናንም ወኪሎች ተወጥተውት በስምምነቱ መሠረት የጠቅላላ የምእመናኑ ተራ ላይ ካህናት “እኛ በቀረበው ላይ መናገር አለብን።” ሲሉ ምእመናን በውስጣቸው ታምቆ የነበረው ፈንድቶ “የኛ ተራ ነው!” ባሉ ጊዜ ኹኔታው ለቁጥጥር የማያመች ነበር። ከዚህ ቀደምም እንደገለጽሁት፦ በዚህ ጊዜ የቀድሞው አለቃ ከዓውደ ምሕረቱ መድረክ ወደ ምእመኑ ሲመጡ ሳይ፦ በነበረብት ኹኔታ ቢወርዱ የሚከተለውን በመፍራት ለመከላከል ስሄድ፦ አንድ በጣም ትሁት፦ ሰላምተኛና ታዛዤ የነበረ ወጣት፡ ፊቱን አጨማድዶ “ርስዎ ደግሞ ምን ሊያደርጉ መጡ?” ያለኝ አይረሳኝም። እንዲሁም ከህቶቻችን “ኮማንደር -ኮማንደር- አይሂዱ! አይሂዱ!” ከሚሉት ውስጥ አንዷ ልብሴን በመጎተት የተማጸነችኝን አስታውሳለሁ። ይህን ያነሳሁበት፦ የቀድሞውን አለቃ ከአፋፉ ላይ ሳገኛቸው “ይህን ኹሉ ያቀነባበሩ ርስዎ ነዎት!” በማለት ወደ ተረበሸው ሕዝብ በጃቸው አመለከቱ። ለካስ ‘ እባክዎ አይሂዱ!’ እያሉ የሚከላከሉኝ በቀድሞው አለቃ እኔን የነገሩ አንቀሳቃሽና የኋላ መሪ አድርገው ያሳድሙብኝ ስለነበር ነው።
ይህ ክብር ለኔ በምንም ምን አይገባኝም። “ከብት ያልዋለበት ኩበት ለቀማ !” ነው። ከዚህ ቀደም በዚቹ ቤ/ክን የተነሳ ስሜ ተጥርቶ ስለነበር አኹንም ለማያያዝ ነው፤፡ ከእውነት የራቀ ኾነባቸው እንጂ።የመጣሁት ከቦካ በኋላ ነው እውነቱን አግኝቼ ለማግባባት ልሞክርም ነውይኸውም ካህናት ‘በተነገረው ላይ መልስ አለን!” ሲሉና ምእመናን በአጽንኦት ሲቃወሙ አበራርጄ ካህናት የጠይቁት እንዲፈቀድላቸው ማድረጌ በቂ ማስረጃ ነበር። የቀድሞው አለቃ ግን ሰውን አሳሳሱት!! በተለይ መዘምራንና አንዳንድ እህቶችን። ይቅር ይበላቸው! ይበለን።

ይህን ክፍል ሳጠናቅቅ በልዩ ማሳሰቢያ ነው፦
 በመጀመሪያ የመጨረሻውን ስብሰባ የመራኸው ለእኩል ሰዓት
ቆሜ ስለሥርዐት! ስለ ስምምነት! ስለ ኅሊና፦ ስለእግዚአብሔር
ብዬ ስማጸን ፍጆታ የከለከልኸኝ ካህን አንዲት ግሩም እህታችንን
ለመጨረሻ ጊዜ ለመሸኘት ደቡብ ለንደን መካነ መቃብር
ስንጠብቅና አስከሬኑን የያዘ መኪና ሲቃረብ ከመኪና ልወርድ
ስከፍት ጉልበቴ ላይ ተደፍትህረጅም ለመሰለኝ ጊዜ የቆየኸው፦
ከኹለታችንም አንድ ትንፋሽ ሳይወጣ የተለያየነውን በተለያዩ ስሜቶች አስተውሳለሁ። ዋናው የኢትዮጵያዊነት መሠረተ ጨዋነት እንዳለህ ነው። ለዚህም አመሰግንሀለሁ።
የሚበልጠው ግን መሠረተ ክርስቲያንነትህ ስለኾነ
ኹለተኛው፡ አንድ በጣም ሰላምተኛና ጨዋ የቅዳሴ ጠበልም ታመጣልኝ የነበርህ ከአሥር ቀናት በፊት መውጫው ላይ ተገኛኝተን “ለምን ርስዎ ደግሞ መጡ?” ብለህ በጠቆረ ፊት ለምን አነጋገርኸኝ ስልህ የመለስክልኝን የመቆርቆር መልስ በምስጋና ተቀብያለሁ። ግን..
ሦስተኛ፡ አንዲት ወጣት መዘምር ችግራችንን በፍጥነት ለመፍታት
“ ከቅዳሴዎቹም አጭሩን፦ ትምሕርቱም ከተነበበው ወንጌል ባጭሩ፦ከሓውርያት አባቶቻችን የወረስነውንከቅዳሴ በኋላ ምእመናን አምጥተው ኹሉም የሚቋደሰውውን ከግሪክኛ “አጋጴ!” (ፍቅር) የተባለውን ካህናት ምእመናንን ትተው በመኮምኮም ብዙ ጊዜ የሚያጠፉትን ሲኾን አቆይተው አልያም ፈጠን ብለው ችግራችንን እንፍታው በማለቴ አንዳንድ ነገር ልታስምሪኝ መጥተሽ “ ኮማንደር-ኮማንደር የሚባሉት ርስዎነዎት? ያልሽኝና ትንሽ የተነጋገርነው
-እንዲሁም አሕዛብ ያላችሁን ሊሎችም የጋራ ችግራችን ግልጽ ያልኾነላችሁ እባካችሁ ሐሙስ የካቲት ፲፩ ቀን (20/03) እምሽቱ ፲፪ ሰዓት (6ፒ ኤም) ኢትዮጵያውያን ተራድኦ ማሕበር ተገናኝተን በአገርና በአንዲት ቤ/ክን ልጅነት እንወያይ። እናንተም የእኛን ዐቅዋምና ምክንያት ትረዱልናላችሁ፦ እኛም የናንትን ከዚያ በኋላ በየዐቅዋማችን በወንማችነት/እህትማማችነት/አባትና – እናት ልጅነት የሰደት ኑሮአችንን እንቀጥላለን። የምን ጠብ፦ የምን ኩርፊያ? ማንን ለማስደሰትና ለመጥቀም?!!?

ተንኮልና፦ ክፋት የተመላባቸው የጠላት መሣሪያዎች እንዳንገናኝ የማይሞክሩት የለም። እናንተ ግን በነፃ አገር በነፃነት የምትኖሩ እንደመኾናችሁ በዐእምሮአችሁ ለኅሊናችሁና ለሃይማኖታአችሁ ታዘዙና ወስኑ።እኔና የእኛን ዐቅዋም ሊያስረዱ የሚችሉ በሰዓቱ ተገኝተን እንጠብቃችኋለን።
አድራሻው 3A, Lithos Rd. (off Finchley Rd) Stations Fichley Rd & Finchley Rd & Busses 13, 82, 113, 187, 268
ፈቃዳችሁ ቢኾን በስልክ ቁትር 0207 794 4265 እንደምትገኙ ብታስታውቁን ይጠቅምውናል።

እሁድ የካቲት ፳፫ ቀን ጠ.ጉ. ተጠርቶ ካስተላለፋቸው ውሳኔዎች ውስጥ
- ጉዳያችን ባስቸኳይ ፍ/ቤት እንዲቀርብና
- ጉዳያችንን አለ አግባብ ሲያሽ ያከረመብንን ያገሪቱን የግብረ ሠናያት ድርጅት (ቻሪቲ ኮሚሽንን) በጥምር ተከሳሽነት እንዲቀርብ ተውስኖአል።

ይህ ማለት ወጪው የትዬ ኤለሌ መኾኑን አጥተነው አይደለም። ተስድደን ካለንበትም መጥተው ትግራይን እንገነጥላለን ባዮችና ግብረ-ዐበሮቻቸው በገንዘባችን የገዛነውን አናስነጥቅም በማለት ነው፤፡ ያገራችን አይበቃም!!?? ሊተባበረን ሊረዳን አብሮን ሊቆም ለሚፈልግ ወገን በ

NatWest Bank, Account name Save St. Mary of London—Sort Code: 60-19-26, Account no. 29112052
ለምትተባበሩን ኹሉ ልባዊ ምስጋናችንን እያስቀደምን ሂደታንን ለማሳወቅ ይመች ዘንድ ማድረጋችሁን በ commanderassefa@yahoo.co.uk
ብትገልጹልኝ አስታውቃችኋለu።

በክፍል ፪ ፦
— በጉዳያችን በገቡት ሊቃነ ጳጳሳት ኮራንባቸው
ወይስ?
— እንደሚሉት የሲኖዶስ ልዑካን ነበሩ ወይስ?
— ሲኖዶስ ዐውቆም ኾነ ሳያውቅ / ፈልጎም ኾነ
ተገድዶ ‘…እንዳያንሠራራ አድርገን
አሽመድምደነዋል..’ ብሎ ከሚፎክርበት ጋር የሚ..?
—ያገራችን ገዥዎች ባለንባት አገር መንግሥት ላይ
ተጽዕኖ እያረጉ ነው ወይስ?
የሚሉትን ዓበይት ጉዳዮች ስለምዳስስ እነምትከታተሉን ተስፋዬ ጽኑ ነው

ወስብሀት ለእግዚአብሔር!

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ታሪክ ሊሆን ነው

$
0
0

ከሰሜን ኮከብ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ክፍል ( ዲፓርትመንት) መዳከሙን ስሰማ በጣም አዘንኩ። ዲፓርትመንቱ እኔ በነበርኩበት ጊዜም ፣ ከዘርና ከሃይማኖት ጋር በተያያዘ፣ ብዙ ችግሮችን ያስተናግድ ነበር። ኢህአዴግ ” ዲፓርትመንቱ የነፍጠኛው መመሸጊያ ዋሻ ሆኗል” በሚል ብሄር ብሄረሰቦች በብዛት እንዲገቡበት ይወተውት ነበር። አንድ የአማራ ተወላጅ ተማሪ ከፍተኛ ነጥብ ቢያመጣም፣ ከሌላው ብሄረሰብ ሰው ካልታጣ በስተቀር፣ መምህር ሆኖ የመቀጠር እድል አልነበረውም። በ1992 ዓም ነው፣ሁለት ሰቃይ ጓደኞቼ መምህር ለመሆን ያመለክታሉ። በጊዜው የዲፓርትመንቱ ሃላፊ የነበሩት ትግራዋይ ዶክተር ፣ሰቃዮቹን ትተው፣ አንድ የኦሮሞ እና አንድ የትግራይ ተወላጅ ምሩቃንን ይቀጥራሉ። አዲሶቹ ተቀጣሪዎች የነበራቸው ድምር ነጥብ ( Cumulative GPA) ጓደኞቼ ከነበራቸው ነጥብ በጣም ያነሰ ነው። በእንዲህ አይነቱ አሰራር ልባቸው የተሰበረው ጓደኞቼም እስከ ሴኔቱ ድረስ ክስ መሰረቱ፣ በመጨረሻ ያገኙት መልስ ግን ” የብሄር ተዋጽዎን ለመጠበቅ ሲባል የተወሰደ እርምጃ ነው” የሚል ነበር።
ለታሪክ ዲፓርትመንት መዳከም ዋናው ምክንያት የዘር ፖለቲካ የትምህርት ስርዓቱን መቆጣጠሩ ነው።
addis ababa un
በታሪክ ክፍለ ጊዜ ተማሪዎች ብሄርና ፖለቲካ ለይተው ሲደባደቡ አስታውሳለሁ ። የተወሰኑ የኦሮሞ ወይም የትግራይ ተወላጆች የተጻፉ ታሪኮችን ወይም ስያሜዎችን ለመቀበል እየተቸገሩ ከአስተማሪዎች ጋር ዘወትር ይጣሉ ነበር ። መምህራን “ማስተማር አልቻንልም” ብለው ስራ እስከማቆም የደረሱበት ጊዜም ነበር። ያም ሆኖ በማይነር ( በሁለተኛ ትምህርት) ከሚማሩት ውጭ፣ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ታሪክ ያጠኑ ነበር ። ታሪክ ለመማር የመጡ ሌሎች አፍሪካውያንና ጥቁር አሜሪካውያንም ነበሩ። ተማሪው ከመብዛቱ የተነሳ ተወዳድሮ የማለፊያ ነጥብ ለማምጣት እጅግ ጭንቅ ነበር። አስተማሪዎችም የተማሪውን ፈተና አርመው በጊዜ ለመመለስ ይቸገሩ ነበር።

አንድ ገጠመኜን ላውጋችሁ። ነፍሳቸውን ይማርና ፕ/ር ሁሴን አህመድ የማጠቃለያ ፈተና ይፈትኑናል። የቀረቡልን ጥያቄዎች 4 ሲሆኑ መልስ መስጠት የሚጠበቅብን ለሁለቱ ብቻ ነው ። ለጥያቄዎቹ መልስ መጻፊያ ይሆን ዘንድ እያንዳንዳቸው 4 ገፆችን የያዙ ሁለት “ሉክ” ወረቀቶች ታደሉ። የጥያቄዎችን ማነስና የገፆችን መብዛት ስመለከት ” ምንድነው የምጽፈው” እያልኩ መጨነቅ ጀመርኩ። እኔ “የሸመደድኩትን” እያጠነጠንኩ ገና አንድ ገጽ ጽፌ ሳልጨረስ ከሁዋላየ የተቀመጠው ተማሪ 8ቱን ገጽ ጨርሶ ወረቀት እንዲጨመረው ጠየቀ፤ ሌሎችም እንዲሁ እያከታተሉ ወረቀት ጠየቁ፣ “በቃ ተሸውጃለሁ” ማለት ነው እያልኩ በድንጋጤ ወረቀቱን ለመሙላት ስል ብቻ እጽፋለሁ። መጀመሪያ ወረቀት ይጨመርንልን ያሉት ጓደኞቼ፣ የተጨመረላቸውንም ወረቀት ጨርሰው በድጋሜ ጠየቁ። አስተማሪውም “የመጨረሻ ወረቀታችሁ ነው” ብሎ አስጠንቅቆ ሰጣቸው። ” ፕሮፌሰር እኔ ጋ አራት የተረፉ ገጾች አሉና ከፈለጉ ልስጣቸው” ለማለት ሲዳዳኝ አንዱ ፈተናውን ጨርሶ ተነሳ፣ በዚህን ጊዜ ልቤ ከሁለት ተከፈለ፣ “ኤፍ” እንደምቅምም ገባኝ። ተስፋ የቆረጠ ሰው ማሰብ አይገደውምና መጻፌን አቁሜ ” እውነት ፕሮፌሰር የዚህን ሁሉ ታማሪ ወረቀት ያርመው ይሆን?’ እያልኩ ከራሴ ጋር ሙግት ጀመርኩ።
ትንሽ ቆይቶ ፕሮፈሰሩ ” you are left with 20 minutes only ” አሉ። በ 20 ደቂቃ ውስጥ፣ አንዳንዴም ቀረርቶ እየጨመርኩበት፣ 7 ገጾችን ጽፌ ለመምህሩ አስተያየት መስጫ ይሆን ዘንድ ግማሽ ገጽ አስተርፌ ተነሳሁ። ” ከሁለት ሳምንት በሁዋላ ፕ/ር ሁሴን ” ከ20 ገጽ በላይ የጻፋችሁ ተማሪዎች ወረቀታችሁን ወስዳችሁ እንደገና ጽፋችሁ አምጡ ብለው ሲያዙ ክፍሉ በሳቅ ተናጋ። እግዚሄር ይመስገን ውጤቱም እንደፈራሁት ሳይሆን ቀረ። ከ14 ዓመታት በሁዋላ ይህ የታሪክ ዲፓርትመንት ሰው አልባ ሆነ። ባለታሪኩዋ አገሬ ታሪክ አልባ ስትሆን ተሰማኝ።

በጎንደር አድማ መርታችኋል የተባሉ 6 ታክሲ ሹፌሮች በእስር ቤት እየተንገላቱ ነው

$
0
0

የጎንደር ከተማ (ፎቶ ፋይል)

የጎንደር ከተማ (ፎቶ ፋይል)


ክሱን ከፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ለማገናኘት የሞከረው ፖሊስ አልተሳካለትም
ምንሊክ ሳልሳዊ :- በጎንደር ከተማ የታክሲ ሹፌሮች የስራ ማቆም አድማ ላይ ተቃውሞ አሰምታችኋል አድማውን መርታችኋል በሚል ሰበብ የታሰሩ 6 ሰዎች እንዳሉ ከአከባቢው የደረሰን ዘገባ ያመለክታል:: ከአንድ ወር በፊት የጎንደር ከተማ የታክሲ ሹፌሮች አዲሱን የትራፊክ የቅጣት ደንብ በመቃወም የስራ ማቆም አድማ መምታታቸውን ተከትሎ አድማውን አስተባብረዋል በሚል ሰበብ ተፈጥሮ ከየመንገዱ ከስራቸው እና ከየቤታቸው ታፍነው የተወሰዱ የታክሲ ሹፌሮች በእስር ቤት ውስጥ እየተሰቃዩ መሆኑን ለወሕኒ ቤት ቅርብ የሆኑ ምንጮች ገልጸዋል::

ባለፈው ሳምንት ፍርድ ቤት ቀርበው የዋስትና መብታቸው ሳይከበር ወደ እስር ቤት የተመለሱት የታክሲ ሹፌሮች ከሰማያዊ ፓርቲ የመጣ ትእዛዝ ነው የስራ ማቆም አድማ ያደረጋችሁት በሚል ጉዳዩን ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር በሃሰት ለማገናኘት በፖሊሶች በሃይል ለማሳመን ጥረት ቢደረግም እንዳልተሳካ ምንጮቹ ገልጸው እስካሁን ምንም አይነት መረጃም ሆነ ማስረጃ መርማሪዎች በማጣታቸው በስራ ማቆም አድማ ላይ የተሳተፉ የታክሲ ሹፌሮችን በታሰሩት ላይ እንዲመሰክሩ በጥቅም እያግባቧቸው መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል::

በአድማው ወቅት የታክሲ ባለንብረቶችም የታሪፍ ማስተካከያ አለመደረጉን በመቃወም የታክሲ ሹፌሮቹን ተቀላቅለው የነበር ሲሆን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባለስልጣናት ሾፌሮቹና ባለንብረቶቹ ወኪል ልከው እንዲነጋገሩ በጊኤው የጠየቁ ቢሆንም ሹፌሮቹ “የክልሉ መንግስት ወከሎችን በተደጋጋሚ የማሰር ልምድ ስላለው ወኪል አንልክም” ብለው እንደነበር ይታወሳል::

የነአርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን አዲስ ሃይማኖት “ቅዱስ ኤልያስ ይዞት የመጣውን መፅሐፍ” ቤተ ክርስትያን እንድትቀበል ጠየቀ

$
0
0

Jemanesh Solomon
ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንደዘገበው የነአርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን አዲስ ሃይማኖት “ቅዱስ ኤልያስ ይዞት የመጣውን መፅሐፍ” ቤተ ክርስትያን እንድትቀበል ጠየቀ። የጋዜጣው ዘገባ እንደወረደ ይኸው፦

መጽሐፉ ለአቡነ ማትያስና ለጠ/ሚ ኃይለማርያም እንዲደርሳቸው ተደርጓል
ደብዳቤው ለእስራኤሉ ጠ/ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታናሁ እና ለተመድ ተልኳል

ከተፃፈ ከ2 ሺህ ዓመታት በላይ አስቆጥሯል የተባለውንና ስለ ቅዱስ ኤልያስ መምጣት ምስጢር የሚተነትነውን መጽሐፍ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተቀብላ ወደተለያዩ ቋንቋዎች በማስተርጎም ምዕመናኖችን እንድታስተምር፣ “ማህበረ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ” ለቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በጻፈው ደብዳቤ ጠየቀ፡፡

ማህበሩ፤የመጽሐፉን ኮፒዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ እና ለብፁዕ አቡነ ማትያስ ህዝቡን እንዲያስተምሩበት ከሚያሳስብ ደብዳቤ ጋር መላኩን አስታውቋል፡፡
አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን አባል የሆነችበት ማህበረ ሥላሴ፤“ቅድስት ቤተ-ክርስቲያን ለሁለት ሺህ ዘመን ስትጠብቀው የቆየችውን ምስጢራዊ መጽሐፍ በአደራ የመረከብና ለዓለም ሁሉ የማሳወቅ ፅኑ ኃላፊነትን ይመለከታል” በሚል ርዕስ ለፓትርያርኩ፣ በግልባጭ ደግሞ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ እንዲሁም ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔትናሁ እና ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት በፃፈው ደብዳቤ “ማህፈድ ብርህት ዘዲዮስቆሮስ አንበሳ” በሚል ርዕስ በግዕዝ ቋንቋ የተፃፈውን መጽሀፍ፣ የቤተ-ክርስቲያኗ ሊቃውንት ተቀብለው ምእመናኑን ስለ ቅዱስ ኤልያስ እና ትክክለኛይቱ ሰንበት እንዲያስተምሩበት አሳስቧል፡፡

ደብዳቤው ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር የተላከው ኢትዮጵያና እስራኤል በመንፈሣዊ አሰራር አንድ ስለሚሆኑበት ሁኔታ ለማመልከት ነው ያሉት የማህበሩ አመራሮች፤ለተባበሩት መንግሥታት የተላከውም መልእክቱ ለዓለም ሁሉ እንዲዳረስ ስለሚፈለግ ነው ብለዋል፡፡
ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት እንደተፃፈ የሚነገርለት መጽሐፉ፤ ስለ ቀዳሚት ሰንበት ምንነትና ዘለዓለማዊነት በግልፅ እንደሚያብራራ እንዲሁም የኢትዮጵያና የእስራኤልን አንድነትና ትንሳኤ ምስጢር ተንትኖ እንደሚያስረዳ ተጠቁሟል፡፡
ማህበሩ በላከው መልዕክት፣ ቅዱስ ኤልያስ ከብሄረ ህያዋን ይዞት የመጣውን መጽሀፍ፣ የቤተ-ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት እንዲመረምሩት፣ በተለያዩ ቋንቋዎች እንዲተረጎምና እንዲታተም፣ ምዕመናንም እንዲያነቡት የማድረግ ግዴታ ፓትርያርኩ እንዳለባቸው ያሳስባል፡፡ “ይህ ሳይሆን በእንቢተኝነትና በቸልታ ለዘመናት በተስፋ የተጠበቀውን ይህን መጽሀፍ እንዳይቀርብ ቢያደርጉ፣ ከብሄረ ህያዋን የመጣው ቀናኢ ነቢይ ዓለምን ሁሉ እየገሰፀ ባለበት ኃያል፣ ስልጣኑ ፅኑ ፈራጅነቱና ቁጣው የሚፈርድ መሆኑን አረጋግጠን እንነግርዎታለን” ብሏል፡፡ “ለቤተ-ክርስቲያኒቱ ሲኖዶስ እና ካህናት ጥፋትና የመጨረሻው ውድቀት ነው” ሲልም ለመፅሃፉ ትኩረት እንዲሰጥ ማህበሩ አበክሮ አሳስቧል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ የፓትርያርኩን ጽ/ቤት እና የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጽ/ቤት በስልክ አግኝተን ለማነጋገር ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

ሕዝባችን ንቁ ነው

$
0
0

እንዴት ጀመራችሁ ከየትስ መጣችሁ
ያረጀ መሣሪያ እንደታጠቃችሁ
ክፋት ምቀኝነት ተንኮሉን አዝላችሁ
እሹሩሩ ልጄ እያባበላችሁ
ህዝብን በማሣሣት ሰይጣን ተጣብቷችሁ
ወይ ለህዝብ ሳይሆን ፍትህ ለተራበው
ችግር ለደቆሰው እርሃብ ለጎዳው ለተጎሳቆለው
አሁን ተረዳነው እራስን መውደድ ነው
በሰይጣን ፈረስ እየጋለባችሁ
በሱዳን ምህታት እያታለላችሁ
ወንድምን በመግደል ወንድምን በማሰር እየፎከራችሁ
አገር ለመገንጠል እየዶለታችሁ
ለአንድነት ለህብረት የቆመውን ሁሉ እየገደላችሁ
የመናገር መብቱን ከህዝቡ ነፍጋችሁ
ውሸት ዲሞክራሱ እያራመዳችሁ
በዘር በሃይማኖት ህዝብን ከፋፍላችሁ
በቋንቋ መሰረት ሃገር በጣጥሳችሁ
ለመንገስ ለመክበር ነበር እቅዳችሁ
የእናንተ ውሸት ባቡር የማይችለው
በከንቱ አትድከሙ ህዝባችን ንቁ ነው
ትዝብት ይታወስ
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር


የስርዓቱ ደጋፊ የሆነችው ድምጻዊት ሃመልማል አባተ ለሁለተኛ ጊዜ ከአሜሪካ አፍራ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰች

$
0
0

በአፍቃሬ ወያኔነቷ የምትታወቀው ድምጻዊት ሃመልማል አባተ አዲስ አልበሟን ለማስመረቅና የተለየያዩ ኮንሰርቶችን ለመሥራት ወደሰሜን አሜሪካ መጥታ የነበረ ቢሆንም በደረሰባት ቦይኮት በተመልካች እጦትና በፕሮሞተሮች መጥፋት አፍራ ወደ አዲስ አበባ መመለሷ ታወቀ።

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ በሰብአዊ መብት ጥሶትና ንጹሃንን በእስር ቤት ያሰቃያል እየተባለ በዓለም አቀፍ ተቋማት ጭምር የሚነገርለትን የወያኔ/ኢሕአዴግ ስርዓት በመደገፍ የምትታወቀው ድምጻዊት ሃመልማል አባተ በዋሽንግተን ዲሲ ከፍተኛ ገንዘብ ወጥቶ በቨርጂኒያ ክሪስታል ከተማ በሂልተን ሆቴል የሲዲ ማስመረቂያ ኮንሰርት አዘጋጅታ 55 ሰዎች ብቻ የተገኙ ሲሆን አንድም አርቲስት በሲዲ ምርቃቱ ላይ አለመገኘቱ አነጋጋሪ ሆኗል። በተለይ በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ በርካታ አርቲስቶች የሚገኙ እንደመሆኑ መጠን በሃመልማል አባተ ሲዲ ምርቃት ኮንሰርት ላይ አንድም አርቲስት አለመገኘቱ ኢቢኤስ የተባለው ቲቪ ሳይቀር እንዳስገረመው በወቅቱ መዘገቡ ይታወሳል።

(ሃመልማል በዲሲ አዘጋጅታቸው የነበረውና በተመልካች ድርቅ የተመታው የሲዲ ምርቃት ኮንሰርት ፍላየር ይህ ነበር)

(ሃመልማል በዲሲ አዘጋጅታቸው የነበረውና በተመልካች ድርቅ የተመታው የሲዲ ምርቃት ኮንሰርት ፍላየር ይህ ነበር)


ሃመልማል በወያኔ/ኢህአዴግ እየተረገጠ ያለውን ሰፊውን ሕዝብን ክዳ ለመሬት ቀሚው፣ ለመሬት ሻጩ፣ ለበዝባዡ፣ ለጨፍጫፊውና ለሰብአዊ መብት ረጋጩ ወያኔ ተቆርቋሪ ሆና በመቅረቧ ከጥቂት ዓመታት በፊት` በጀርመን ሃገር የሙዚቃ ኮንሰርት አዘጋጅታ ሕዝቡ ቦይኮት በማድረጉ 18 ሰዎች ብቻ የተገኙ ሲሆን ከ3 አመት በፊትም እንዲሁ ወደ ሚኒሶታ በመምጣት ኮንሰርት አዘጋጅታ ከ12 ያነሰ ሰው ብቻ በመገኘት በተመልካች ድርቅ ተመትታ ወደ ሃገሯ ተመልሳለች፤ ያሉት የመረጃ ምንጮች ሃመልማል ከስርዓቱ ጋር ያላት የጥቅም ግንኙነት የተረሳላት መስሎ ወደ አሜሪካ በድጋሚ ብትመጣም በዋሽንግተን ዲሲ 55 ሰዎች ተግኝተው አሳፍረዋታል። በዲሲ ኮንሰርት ሲዘጋጅ እስከ 5 ሺህ ሰው እንደሚገባ ልብ ይሏል።

ሃመልማል በዳላስ ከተማ በፋሲል ደመወዝ ስም በመጠቀም፤ (ሕዝቡ የፋሲል ደመውዝ አድናቂ በመሆኑና እርሱን ተከትሎ በመግባቱ) በኮንሰርቱ ላይ ቁጥሩ ጨመር ያለ ሰው ቢገባም በሎስ አንጀለስ ከተማ የቀድሞ ባለቤቷ እና የልጇ አባት በሚያስተዳድረው ሮዝሊን የሲዲ ምርቃትና ኮንሰርት ብታዘጋጅም በተመሳሳይ ቦይኮት ተደርጋ በተመልካች ድርቅ ተመትታለች። በዚህም ሞራሏ የተሰበረው ሃመልማል ከስህተቷ ተምራ ወደ ሕዝብ ከመመለስ ይልቅ ወደ ሃገር ቤት በመመለስ ነገሩን ለማብረድ ብትሞክርም እንዲህ ያለው ቦይኮትና በየከተማው ያሉ ፕሮሞተሮች ያለመጋበዝ ትግል ታግዞበት ወደ ሃገሯ ልትመለስ በቅታለች።

ዲያስፖራው ከወያኔ ጋር በጥቅም የተሳሰሩ ድምጻዊያንን ቦይኮት ማድረጉ የሚያስመሰግን ነው የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች ይህ ጉዳይ በርትቶ ሊቀጥል እንደሚገባው አስታውቀዋል። እነዚሁ አስተያየት ሰጪዎች የስርዓቱ ደጋፊ የሆኑ አርቲስቶች በሃገር ቤት ከወያኔ ጋር በመሞዳሞድ የሚያገኙት ጥቅም ውጭ ሲመጡ ሊያገኙ አይገባም ይላሉ። ዲያስፖራው ሃገሩን የሚያከብረውን አርቲስት እንደሚያክብረው ሁሉ ከወያኔ ጋር ለሆዱ ያደረውን ድምጻዊም በማግለል ተመልካች አልባ ማድረግ እንደሚገባው አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።

ከሃመልማል አባተ ውጭ ነዋይ ደበበ፣ ሰለሞን ተካልኝና የመሳሰሉት ድምጻዊያን በዲያስፖራው ኪሳራ እንደደረሰባቸው ይታወሳል።

አንድነት እና መኢአድ የፊታችን ሐሙስ መጋቢት 11 ቀን 2006 ዓ.ም የቅድመ ውህደት ፊርማ ሊፈራረሙ ነው

$
0
0

UDJ
aeup
የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤትና የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት አባላት በጋር ባካሔዱት ስብሰባ ሁለቱ ፓርቲዎች የፊታችን ሐሙስ መጋቢት 11 ቀን 2006 ዓ.ም የቅድመ ውህደት ፊርማ እንዲያደርጉ መመሪያ ማስተላለፋቸውን ስብሰባውን የተከታተለው የፍኖተ ነፃነት ባልደረባ ዘገበ፡፡

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አባላት እና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ላዕላይ ምክር ቤት አባላት ዛሬ መጋቢት 7 ቀን 2006 ዓ.ም በመኢአድ ጽ/ቤት ባደረጉት ስብሰባ የሁለቱ ፓርቲዎች በአስቸኳይ እንዲዋሀዱ መመሪያ ያስተላለፉት ሁለቱን ፓርቲዎች ፓርቲዎች ለማዋሀድ እያሸማገሉ የሚገኙ ምሁራንና ታዋቂ ግለሰቦች የተካተቱበት ኮሚቴ ያቀረባቸው የማስማሚያ ነጥቦች ከቀረቡ በኋላ እና የሁለቱም ፓርቲዎች ፕሬዘዳንቶችና የውህደት ኮሚቴ አባላት ውህደቱ የዘገየበትን ምክንያት ከዘረዘሩ እንዲሁም የሁለቱ ፓርቲዎች ምክር ቤት አባላት ሰፊ ውይይትና የመፍትሔ ሀሳብ ካቀረቡ በኋላ ነው፡፡ የቅድመ ውህደት ፊርማው በሚፈረምበት ዕለት ሁለቱም ፓርቲዎች የውህደቱን ሂደት የሚያመቻቹ ወኪሎቻቸውን እንደሚያሳውቁም የፍኖተ ነፃነት ባልደረባ ዘግቧል፡፡

ኃይለማርያም ደሳለኝ እና አባዱላ ገመዳ ከ”ተንባዩ”ጋር ታዩ፤ “ቡራኬ ሰጥቻቸዋለሁ”ይላል (ፎቶ ተይዟል)

$
0
0

”ትንቢተኛው” ከጠቅላይ ሚኒስትራችን ጋር ምን ይሰራል ?
tenquayu
ከአቤ ቶኪቻው

ሰሞኑን ጠቅላያችን አንዴም ሲደንሱ አንዴም ”ሲቀደሱ” በየሚዲያው እያየናቸው ነው። እሰይ እንዲህ ነው እንጂ የኔ አንበሳ በዬ ላደንቃቸው እፈልጋለሁ። ይሄንን ፎቶ ያገኘሁት ከፌስ ቡክ ተሰውረው በትዊተር የመሽጉ ጎበዞች ዘንድ ነው። ከዛም በማስፍንጠሪያ ተስፈንጥሬ ”ትንቢተኛው” ድረ ገጽ ውስጥ ብገባ በኢትዮጰያ ቆይታው አባ ዱላ ገመዳ እና ሃይለማሪያም ደሳለኝን ጨምሮ ለሌሎችም ባለስለጣኖች ቡራኬ እንደሰጠ ይናገራል።

እግረ መንገዱን ባለስልጣኖቻችን እስር እና ግርፉን እንዲተዉ ስልጣንም ከእግዜር እንጂ ከጠብ ምንጃ ዘንድ እንዳልሆነ ነግሮልን ከሆነ ደህና ነው!

ዝም ብሎ የወደፊት እጣ ፈንታቸውን ብቻ ነግሯቸው ከተመለሰ ግን ዝም ብሎ ነው የለፋው፤ የባለስልጣኖቻችንን እጣ ፈንታ እኛም እንነግራቸው ነበር። (አያያዙን አይቶ… ) እንዲል የሀገሬ ሰው ማለት ነው።

ማላዊውን ትንቢተኛ እንደኔ ለማታውቁት ከዩቲዩብ ላይ ያገኝሁት አንድ ስራውን በድረ ገጻችን ውስጥ እንደሚከተለው አሰቀመጠዋለሁ፤

የምር ግን ለጠቅላያችን እና እና ለአባዱላችን ምን ተንብዮላቸው ይሆን… ?

በቪዲዮው ውስጥ አንዷን ደርባባ (ማሊያዊት ሳትሆን አትቀረም) ከአንድ እውቅ እና ትልቅ የኢትዮጵያ ባለስልጣን ጋር የፍቅር ቁርኝት መስርታ እንደነበር ህዝብ ፊት ሲነግራት አይቼ ያ ባለስልጣን ማን ይሆን… ብዬ ለማወቅ ጓጓቴንም አልደብቅዎትም፤ ማን ያውቃል ባላየነው ቪዲዮ ደግሞ ባለስልጣኖቻችንን ከማላዊት ኮረዳ ጋር ፍቅር የመሰረትክ ውጣ… ብሎ አስለፍልፏቸው ይሆናል።

ጭማሪ፤
ባለስልጣኖቻችን ግን እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ”በበረከቱ ይጎብኛት” ሲባል እንደዛ እንዳልሳቁ ዛሬ ምን ታያቸው… ወይስ የኢትዮጵያ እግዜር እና ”የትንቢተኛው” እግዜር ይለላያያሉ… ?

ብርሃኑ ተዘራ (ላፎንቴን) በሚኒሶታ የተሳካ የሙዚቃ ኮንሰርት አቀረበ

$
0
0

tezera
(ዘ-ሐበሻ) ተበቺሳ የተሰኘውን አልበሙን በቅርቡ የለቀቀው ድምፃዊ ብርሃኑ ተዘራ (ላፎንቴን) በሚኒሶታ ትናንት ማርች 15 ቀን 2014 ዓ.ም የተሳካ የሙዚቃ ኮንሰርት አቀረበ።

በእናት ኢንተርቴይመንት እና በዲጄ ቢኬ አስተናጋጅነት በሚኒሶታ ራስ ላውንጅ በተደረገው የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ ብርሃኑን ለማየት በርካታ የሚኒሶታ ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን በሙዚቃውም መደሰታቸውን ከተለቀቁ ቪድዮዎች መረዳት ይቻላል። ብርሃኑ አማርኛ፣ ኦሮሚያ፣ ትግርኛና ሌሎች የኢትዮጵያ ብሔረሰብ ሙዚቃዎችን የተጫወተ ሲሆን በተለይ “አምበሳው አገሳ” የሚለውን ሙዚቃ ሲጫወት የሚኒሶታ ነዋሪ የአንድነት ስሜቱን መቆጣጠር ተስኖት ሲፈነጥዝ ዘ-ሐበሻ የቀረጸችው ቪድዮ ያሳያል።

አርቲስት ብርሃኑ ተዘራን ከኮንሰርቱ በኋላ ዘ-ሐበሻ አነጋግራው በሚኒሶታ የተደረገለት አቀባበል ያማረ እንደነበርና ከፍተኛ ሕዝብ በኮንሰርቱ ላይ በመገኘቱ መደሰቱን ጠቁሟል።

ከብርሃኑ ተዘራ ጋር ያደረግነውን ቃለምልልስ እስከምናቀርብ ከሙዚቃ ኮንሰርቱ ቪድዮ አንዱን እንጋብዛችሁ።

[የሃረሩ ቃጠሎ ጉዳይ] መቃጠል መቃጠል መቃጠል –ከፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)

$
0
0

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም

ከአስራ ምናምን ዓመታት በፊት ፔሩቪያዊው ኢኮኖሚስት ሄርናንዶ ደ ሶቶ ስለ “ኢንፎርማል” ኢኮኖሚ በጻፈው መጽሃፍ ውስጥ ፣ በአለም ላይ በህጋዊ መንገድ ያልተዘመገበ ከ10 ትሪሊየን ዶላር በላይ ሃብት መኖሩን፣ ይህን ሃብት መዝግቦ የባለቤትነት ህጋዊ መብት በመስጠት ብዙ ዜጎችን ከድህነት ማውጣት እንደሚቻል ገልጾ ነበር። ደ ሶቶ እንደሚለው በደሃ አገራት ሁለት አይነት ኢኮኖሚ አለ። አንደኛው ጥቂቶች የሚያንቀሳቅሱትና በመንግስት እውቅና የተሰጠው ኢኮኖሚ ሲሆን ሌላው ደግሞ መንግስት የማያውቀው በአብዛኛው ህዝብ የሚንቀሳቀሰው ኢኮኖሚ ነው ፤ ይህ ኢኮኖሚ በመንግስት እውቅና ያልተሰጠው በመሆኑ በዚህ ስር የታቀፉ ዜጎች ከባንክ ተበድረው ቢዝነሳቸውን ለማስፋፋት አይችሉም፤ መንግስትም ከእነዚህ ሰዎች ተገቢውን ታክስ አያገኝም። በደሃ አገራት ውስጥ መንግስታት እውቅና ሳይሰጡት የሚንቀሳቀሰው ሃብት እውቅና ከተሰጠው ሃብት ይበልጣል። ደ ሶቶ እንደሚመክረው ህጋዊው የኢኮኖሚ ስርአት የማያውቃቸውን ሀብቶች በመመዝገብና ህጋዊነት በማላበስ ዜጎች ሃብትና ንብረት እንዲያፈሩና ድህነትን እንዲሻገሩ ማድረግ ይቻላል።

የ ደ ሶቶን ሃሳብ ለማየት በአዲስ አበባ የተገነቡ የጨረቃ ቤቶችን እንመልከት። ነዋሪዎቹ ቤቶችን ለመስራት ብዙ ገንዘብ፣ ጉልበትና ጊዜ አፍስሰዋል፣ ይሁን እንጅ የመንግስትን የባለቤትነት ማረጋገጫ ቁራጭ ወረቀት ለማግኘት ባለመቻላቸው የሰሩት ቤት ሃብት ሊሆን አልቻለም። ቤታቸውን መሸጥ፣ መለወጥ እንዲሁም በባንክ አስይዘው ገንዘብ መበደር አይችሉም። እነዚህ ሰዎች የባለቤትነት ካርታ እስካላገኙ ድረስ ቤታቸው ሃብታቸው ነው ማለት አይቻልም። ነገር ግን የይዞታ ማረጋገጫ ብጣሽ ወረቀት ባገኙ በሰከንድ ውስጥ ቤታቸው ሃብታቸው ይሆናል፣ መሸጥ መለወጥ፣ ቤታቸውን አስይዘው ከባንክ መበደር ይችላሉ። በአንድ ወረቀት የቤቶቹ ባለቤቶች ከድህነት ወደ ሃብት ባለቤትነት ተሸጋገሩ፣ በሌላ አነጋገር የድህነትን መጋረጃ ቀደዱ ማለት ነው። መንግስት ህጋዊ እውቅና ለሌላቸው ሌሎች ቢዝነሶችም ህጋዊ እውቅና ቢሰጥ ፣ ሰዎችን ባለሀብት ማድረግ ብቻ ሳይሆን መንግስትም ከእነዚህ ቢዝነሶች ብዙ ግብር መሰብሰብ ይችል ነበር። በኢትዮጵያ ያለው የገዢዎች ስብስብ ግን ንብረት በማውደም የሚደሰት ይመስላል። ቤት ማፍረስና ንብረት ማቃጠል ልዩ መልክቱ ሆኗል። ባለፉት 22 ዓመታት ስንትና ስንት ቤቶች ፈረሱ፣ ስንቶቹ ተቃጠሉ፣ ስንትና ስንት የአገር ሃብት አብሮ ወደመ፣ ስንቶቹ ደኸዩ፤ ወረቀት በማደል ህጋዊ ማድረግ ሲቻል ሳይቻል ቀረ።

ከረጅም አመታት በሁዋላ የደ ሶቶን መጽሃፍ እንዳስታውስ ያደረገኝ በሀረር በተደጋጋሚ የሚታየው የእሳት ቃጠሎ ነው። የንግድ ቤቶችን የሚያቃጥላቸው መንግስት ከሆነ የመንግስት የድንቁርና ብዛት ልክ ማጣቱን የሚያመለክት ነው። መንግስት ቤቶችን ሲያቃጥል፣ ቤታቸው የተቃጠለባቸው ሰዎች ወደ ድህነት ጎራ መግባታቸውን አያውቅም ለማለት አልደፍርም። እነዚህ ሰዎች ህጋዊ እውቅና የላቸውም ቢባል እንኳን፣ የህጋዊነት ማረጋገጫ ብጣሽ ወረቀት በመስጠት፣ ህጋዊ በማድረግ ድህነትን እንዲሻገሩ ማድረግ ይቻል ነበር። ንብረትን በእሳት በማጋየት የሚገኝ የኢኮኖሚ እድገት ምን እንደሆነ በፍጹም አይገባኝም፤ የማውደም ኢኮኖሚክስ የሚባል ነገር መኖሩንም አላውቅም።
Harar City
መንግስት አነስተኛና ጥቃቅን እንዱስትሪ የሚለው ነገር አለ። ሃሳቡ ፖለቲካዊ ይዘት ባይኖረው ጥሩ ነው። አውሮፓኖች ያደጉት በተለያዩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች በጊዜው አጠራር ( ጊልዶች) ነው። የዛሬዎቹ ግዙፍ የአውሮፓ ኢንዱስትሪዎች በተለያዩ አነስተኛ ጊልዶች የተመሰረቱ ናቸው። በእኛ አገር ግን መንግስት ጥቃቅንና አነስተኛ የተባሉትን ድርጅቶች ከቢዝነስ አውጥቶ የፖለቲካ ስራ ስለሚያሰራቸው ተደካሙ፣ እነዚህ ድርጅቶች የቢስነዝ ድርጅቶች ከሚባሉ፣ ጥቃቅንና አነስተኛ የፖለቲካ ድርጅቶች ቢባሉ ይቀላል። መንግስት እነዚህን ድርጅቶች በመደገፍ ወደ መለስተኛ እንዱስትሪነት እንዲለወጡ ከማበረታታት በራሱ ትላልቅ ግንባታዎችን ያካሂዳል። አምባገነን መንግስታት ሁሌም ትላልቅና ብልጭልጭ ግንባታዎችን መስራት ያስደስታቸዋል። ግንባታዎቹ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ይኑራቸው አይኑራቸው፣ በህዝቡ እስከታዩና “ ዋው” እስካስባሉ ድረስ ግድ የላቸውም። ለምሳሌ የተከዜን የሃይል ማመንጫ እንመልከት። የወጣበት ገንዘብ የትየለሌ ነው፣ ጠቀሜታው ግን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም ፣ ግልገል ጊቤም እንደዛው ነው። በአባይ ግድብ ኢኮኖሚያዊ አዋጭነት ላይም ጥርጣሬ አለኝ- በተለይ ከደለል ጋር በተያያዘ የሚፈጠረው ችግር በቀላሉ አይፈታም። በአዲስ አበባ የሚገነባው ባቡር ብዙ ጦሶችን ይዞ እንደሚመጣ እድሜ ከሰጠን እናየዋለን። መንግስት ለታይታም ቢሆን በሚያስገነባቸው ግዙፍ ግንባታዎች አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች ተረስተዋል፣ በዚህም የተነሳ እድገቱ መሰረት የሌለው የእቧይ ካብ ሆኗል።

በሃረርና በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ነጋዴዎችን ንብረት ከማውደም በአነስተኛ ማህበራት እያደራጁ የኢኮኖሚው መሰረት እንዲሆኑ ማድረግ ይቻል ነበር፤ ነገር ግን ለዜጎቹ የሚቆረቆር መንግስት የለምና ሁሉም ነገር በምኞትና በነበር ይቀራል።
harar city fire

የጠፋውን የማሌዥያ አውሮፕላን የበላው ጅብ አልጮህ አለ፤ (ከዚህ በፊት 5 አውሮፕላኖች ጠፍተው እንደነበር ያውቁ ኖሯል?)

$
0
0

ከአትላንታው አድማስ ራድዮ

ስለ ማሌዢያው የበረራ ቁጥር 370፣ የተሰወረ አውሮፕላን መዘገብ እጅግ ከባድ ነው። ምክንያቱም ነገሮች በየደቂቃው ይቀያየራሉና። ገና ሲጀመር፣ አውሮፕላኑ ለመጨረሻው ጊዜ ድምጽ ያሰማበት ሰአት ልክ አልነበረም፣ ከዚያ ቀጥሎ ሁለት ጥቁሮች በሃሰት ፓስፖርት ተሳፍረዋል ተባለ፣ ጥቂት ቆይቶ ጥቁር አይደሉም፣ ኢራናውያን ናቸው ተባለ፣ .. ከዚያ በኋላ 6 ሰዎች አውሮፕላኑ ውስጥ ሊገቡ ካሉ በኋላ ሃሳባቸውን ቀይረዋል ተባለ፣ ጥቂት ቆይቶ ስድስት አይደሉም 2 ናቸው፣ እነሱም ገና ከቤታቸው ሳይወጡ ሃሳባቸውን የቀየሩ ናቸው ተባለ ….፣ ከዚያ ደግሞ አውሮፕላኑ ከጠፋ ከ 48 ሰአት በኋላ የአንዳንድ ተሳፋሪዎች ስልክ ይጠራል ተባለ . ጥቂት ቆይቶ ፣ ውሸት ነው የማንም ስልክ አይጠራም ተብሎ ተነገረ …፣ ከዚያ በኋላ ቻይናዎች በአንድ የቻይና ባህር ላይ የአውሮፕላኑ ስባሪን አይተናል አሉ ተባለ ..፣ ጥቂት ቆይቶ ውሸት ነው አላዩም በሚል ተስተባበበለ።
Malaysia-Airlines
እያንዳንዱ የሚነገር ጉዳይ ልብ የሚያንጠለጥል ቢሆንም፣ በዚህ በዓለማችን የበረራ ታሪክ እጅግ ውስብስብና አሰገራሚ የሆነ መሰወር ጉዳይ ሁሉም መላምቱን ለመስጠት ቢቸኩል የሚፈርድ አልነበረም። እንደተባለው አውሮፕላኑ በቴክኒክ ችግር አይደለም ድምጹን ያጠፋው፣ እንደተባለው ካቅሙ በላይ የሆነ ነገር ገጥሞትም አይደለም።

ምናልባት ያለፉትን ሰባት ቀናት የተለያዩ ነገሮችን ሰምታችሁ ይሆናልና ቀጥታ ወደፊት በመፈናጠር ዛሬ ጉዳዩ ከደረሰበት ነገር እንጅምር። ከዚያ በኋላ ከዚህ በፊት የጠፉ አውሮፕላኖችን ታሪክ እናሳያችኋለን።

ዛሬ ጠዋት የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትርና የአየር ሃይል ሃላፊያቸው ያሉበትን ደረጃ ለመናገር ብቅ ብለው ነበር። በነሱ መረጃ መሰረት ዛሬ የተነገረው ትልቁ ነገር አውሮፕላኑ በቴክኒካል ችግር ሳይሆን ሆን ተብሎ ድምጹን ማጥፋቱንና ፣ ምናልባትም የመጨረሻውን ግንኙነት ከተቆጣጣሪዎች ጋር ካደረገ በኋላ ቢያንስ 7 ሰአት ያህል ሳይበር እንዳልቀረ መናገራቸው ነው፡፡ ያ ማለት አውሮፕላኑ ተጠልፏል ወይም ታግቷል። ይህ የሆነው ደግሞ ወይም ከተሳፋሪዎች መካከል በአንዱ ወይም ደግሞ እንደ ኢትዮጵያው አየርመንገድ በራሱ ፓይለት ተጠልፎ ነው ማለት ነው።

ይህ የዛሬው ውጤት እስካሁን አውሮፕላኑ ሲፈለግ የነበረባቸውን ቦታዎች ሁሉ ፉርሽ እንደነበሩ የሚያሳይ ነው። ለመሆኑ አውሮፕላኑ ከምድር ተቆጣጣሪዎች ጋር እንዳይገናኝ፣ ሆን ብሎ መገናኛውን የነቀለው ሰው ማነው? ይህ ሊሆን የሚችለው እንደ አቪየሽን ሃላፊዎች ወይ በራሱ በፓይለቱ ነው፣ ወይም ደግሞ በጣም ጥሩ የሆነ የፓይለትነት ችሎታ ባለው ጠላፊ ነው። ይህ ከሆነ ደግሞ አውሮፕላኑ ቢያንስ ለሰባት ሰአት ያህል በምዕራብ አቅጣጫ ከተጓዘ ሊደርስ የሚችለው ሁለት ቦታ ነው፣ አንዱ አንዳማን ደሴቶች ሲሆን ሁለተኛው ህንድ ውቂያኖስ መካከል ነው። እንደ ማሌዥያ ባለሥልጣኖች ገለጻ አውሮፕላኑ የያዘው ነዳጅ ቢያንስ ሰባት ሰአት ያህል ያስኬደዋል። ያ ማለት ከዚያ በላይ መሄድ ስለማይችል፣ ወይም አንዱ የተደበቀ ደሴት አርፏል፣ ወይም ህንድ ውቂያኖስ መካከል ተከስክሷል። አሁን ያለው መላ ምት ይህ ነው።

ይህም ቢሆን እንቆቅልሹን የሚፈታው አይደለም። ለመሆኑ ከአየር መንገዱ ጋር ከ1981 ዓ.ም ጀምሮ የቆየው ፓይለት፣ የቤተሰብም የሆነ የሌላ ችግር ያልታየበት፣ .. ጥሩ ምግባር እንዳለው የተመሰከረለት፣ በትዳሩ ከ20 ዓመት በላይ የቆየው ፓይለት እንዴት ሆን ብሎ አውሮፕላኑን ይዞ ይሰወራል? ይህ አንዱ ጥያቄ ነው፡ በሌላ በኩል የ 27 ዓመቱ ረዳት ፓይለት አብዱል ሃሚድ፣ ከአየር መንገዱ ጋር ለ7 ዓመት ሰርቷል፣ የተከበረና ምንም አይነት የሚያጠራጥር ነገር የለሌበት ነው። ርግጥ ከዓመታት በፊት ከተሳፋሪዎች መካከል ሁለት ሴቶችን ውስጥ ድረስ ጋብዞና አጠገቡ አስቀምጦ መጓዙ ቢነገርና ይህም የአየር መንገድ ህግን መተላለፍ ቢሆንም፣ በጉርምስና ተሳብቦ ከመቅረቱ በቀር ሌላ እንዲህ ያደርጋል ተብሎ የሚያስገምት ነገር ምንም አልተገኘም።

ከመንገደኞች መካከል ከሆነስ የአውሮፕላን እገታው የተደረገው ማን አደረገው? ለምንስ አደረገው? ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው። ከመንገደኞቹ አብዛኞቹ ቻይኖች እንደመሆናቸው አልቃይዳና ታሊባን በዚህ ድርጊት ይኖራሉ ብሎ ማሰብ ከባድ ነው። ርግጥ አንዳንድ ተንታኞች ከቻይና አንድ ግዛትን ለመገንጠል የሚታገልና ከዚህ በፊት አንድ የቻይና አውሮፕላን ለመጥለፍ የሞከረ አንድ ድርጅት እንዳለ በማስታወስ ይመዝገብልን እያሉ ነው። አስገራሚው ነገር ግን፣ ይህ ከሆነ ጠላፊዎቹ ወይም አጋቾቹ ወይም ድርጊቱ የፈጸመው ማንም ይሁን ማን፣ እንዴት ምክንያቱንና የሚፈልገውን አልተናገረም? እንዲሁ ዝም ብለን እንሙት፣ ድምጻችንን እናጥፋ ብሎ እንዴት ይወስናል? ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው።

ነገር ግን አሁን ባለው የነገሮች ግጥምጥም አውሮፕላኑ የቴክኒክ ብልሽት አልገጠመው ይልቁኑ ሆን ተብሎ ታግቶ ወይም ፓይለቱ ራሱ አግቶት የሆነ ቦታ ወስዶታል ወይም ውቂያኖስ መካከል ከስክሶታል። ይህ ደግሞ በቅርብ ከሆነውና የራስን አውሮፕላን ጠለፈ ከተባለው የኢትዮጵያው ሃይለመድህን ታሪክ ጋር ለማመሳሰል የሞከሩም ነበሩ።

ከዚህ በፊት የጠፉ አውሮፕላኖች ተገኝተዋል? የጠፉስ አሉ?

አዎ አሉ።
- ለምሳሌ በሜይ ወር 2003 ዓ.ም የኡጋንዳ ንብረት የሆነው ቦይንግ 727 ድንገት ሳይፈቀድለት ከአየር ማረፊያው ተነስቶ በመብረር ያልታወቀ ቦታ ሄዷል – እስካሁንም የት እንደገባ አልተገኘም። ፓይለቱና ረዳቱ ብቻ እንጂ ተሳፋሪ አልነበረውም።
- የፈረንሳይ አየር መንገድ በረራ ቁጥር 447 በ2009 ዓ.ም ድንገት ጠፍቶ ፣ ስብርባሪው ህንድ ውቂያኖስ ላይ የተገኘው ከሁለት ሳምንት በኋላ ነበር።
- የትራንስ ዎርልድ አየር መንገድ ንብረት የሆነው አውሮፕላን በበረራ ቁጥር 800 ጉዞ ከጀመረ በኋላ አየር ላይ በመፈንዳቱ 230 ሰዎች አልቀዋል። ይህ የሆነው በ1996 ዓም. ነው።
- የታይገር አየር መንገድ ንብረት የሆነው አውሮፕላን ፣ በበረራ ቁጥር 793 ጉዞ ከጀመረ በኋላ 106 ሰዎችን እንደጫነ የት እንደገባ አልታወቀም ፣ ይህ ይሆነው በ1962 ዓ.ም ቢሆንም፣ ዛሬም ድረስ ምን እንዳጋጠመው የሚያውቅ የለም።
- በ1957 ዓ.ም የፓን አሜሪካ አየር መንገድ አውሮፕላን ቦይንግ 337 44 ሰዎችን እንደጫነ አየር ላይ ጠፋ፣ከአንድ ሳምንት በኋላ ስብርባሪው ውቂያኖስ ላይ ተገኘ።

እነዚህ ሁሉ አስገራሚ ታሪኮች ናቸው። አንዳንዶቹ ምናልባት ቴክኖሎጂ በጣም ባልዳበረበት ወቅት ሊሆኑ ይችላሉ። አሁን 43 መርከቦች፣ 58 አውሮፕላኖች፣ 14 አገሮች ፍለጋውን እያጣደፉ ቢሆንም፣ የመጥፋቱ እንቆቆልሽ ግን ፣ አገር ስጠኝ ብለን የምንፈታው አልሆነም።

Hiber Radio: የወቅቱን የኢትዮጵያውን አገዛዝ ጨምሮ ምዕራባውያን ለአምባገነኖች የሚሰጡት ድጋፍ ተገቢ አለመሆኑን አንድ አሜሪካዊ ምሁር ገለጹ

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ መጋቢት 7 ቀን 2006 ፕሮግራም
>

አቶ አገኘሁ መኮንን የድንበር ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የም/ቤት አባል ለሱዳን ስለተሰጠው የአገራችን መሬት ለህብር ከስዊዘርላንድ ከሰጡት ቃለ መጠይቅ(ሙሉውን ያዳምጡት)

<...>

አቶ ግርማይ ግዛው የአንድነት የሰሜን አሜሪካ የድጋፍ ማህበር ሊቀመንበር ስለ አዲሱ የሚሊዮኖች ድምጽ ሁለተኛ ዙር እንቅስቃሴ ከሰጡን ቃለ ምልልስ የተወሰደ

<...>

አቶ ሰለሞን በቀለ በቬጋስ የአንድነት የድጋፍ ቻፕተር ሰብሳቢ

<...>>

አቶ ኤልያስ ረሺድ በስዊዘርላንድ የአድዋ በዓል አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ትላንት ስላደረጉት በጄኔቭ የአድዋ በዓል አከባበር አስመልክቶ ለህብር ከሰጡት ቃለ መጠይቅ

>

አቶ ኦባንግ ሜቶ ከጄኔቭ ለህብር ከሰጡት ቃለ መጠይቅ(ሙሉውን ያዳምጡት)

የሩሲያና የዩክሬን ውዝግብና የቀረው ምዕራብ አለም ከሩሲያ ጋር የገባበት ፍጥጫ(ልዩ ዘገባ)

>

ዶ/ር ኤፍሬም መኮንን ከአትላንታ ስለ ኦባማ ኬር ከሰጡት ማብራሪያ

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

የወቅቱን የኢትዮጵያውን አገዛዝ ጨምሮ ምዕራባውያን ለአምባገነኖች የሚሰጡት ድጋፍ ተገቢ አለመሆኑን አንድ አሜሪካዊ ምሁር ገለጹ

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ካልተከበረ ልማት የሚባለው ዘለቄታ እንደሌለው ገለጹ

ጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ አንድ ሺህ ቀናቶች በእስር ቤት አሳለፈች

ኤርትራ ህገ ወጥ ብላ ካሰረቻቸው የመናውያን አሳ አስጋሪዎች የተወሰኑትን ለቀቀች

ከሳውዲ የኢትዮጵያውያንን ሰቆቃ እየተከታተለ የሚዘግበው የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ዘጋቢ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በአገሪቱ የደህንነት ሰዎች መታሰሩ ተሰማ

አንድነትና መኢአድ ሐሙስ የቅድመ ውህደት ፊርማ ለማድረግ ወሰኑ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ


ሃገራዊ ጥሪ ከ 2007 ምርጫ በፊት!

$
0
0

ስለ ሃገራችን ኢትዪጵያ መከራ፣ ስለ ህዝባችን ስቃይ፣ ስለ ኢህኣዴግ ግፍ፣ ስለ ተቃዋሚዎች ህብረት ኣልባ መሆን፣ ሌላም ሌላም ከሚገባው በላይ ተጽፈዋል፣ ተነግረዋል፣ ነገር ግን ያመጣነው ለውጥ የለም – እንዲያውም የባሰ መለያየት፣ መወቃቀስ፣ ማጥላላት፣ እና የኢህኣዴግን ኪስ እንዲሰፋ ኣስተዋጽኦ ኣድርገናል። ኣሁንም ኣሁንም ለውጥ ከተፈለገ እኛ ራሳችን መለውጥ ኣለብን: የሃገር ሃገራዊ ራእይ ኣግኝተን መስማማት የግድ ይላል።

ኣሉታዊ ኣስተዋጽኦ
በብልጣብልጥ እና በኣጭር ጊዜ ስልጣን ለመጨበጥ የሚደረገው ሩጫ ካለፈው 20 ኣመት እንዳየነው የትም ኣያደርስም። ለስልጣን መውጣጫ የሚደረጉ ኣስመሳይ ፈጠራዎች ሁሉም ነቅቶባቸዋል፣ ሰዎች ዝም ይበሉ እንጂ በልባችው መሳቃቸው ኣልቀረም። በዘር፣ በጎሳ፣ በጥቅማጥቅም ወዘተ የሚደረጉ ስብስቦችና መሳጥሮች ስንቶችት በታትነዋል:: በኣንጻሩ ደግሞ ኢሕኣዴግን ከነበረው ደካማነት ኣጠናክረውታል።

ስለዚ መጠላለፉ እና ሩጫው ይቅርና ረጋ ብለን ተሰባስበን፣ ተነጋግረን፣ ተመካክረን፣ ላይ ታች ብለን፣ ግዝያዊ የሃገር ኣመራር መመስረት የግድ ይላል። ወደ ሌላ ውጥን ሳንሄድ በቅድሚያ ያሉትን ድርጅቶች ተሰባስበው ግዝያዊ የሽግግር መድረክ እና ስርኣት – መመስረት ኣለባቸው። ከፓሪስ ኮንፈረንስ፣ ከኢድሃቅ ፣ ከህብረት፣ ከቅንጅት….መማር መቻል ኣለብን።

ስላለው የድሮ ታሪካችን ብቻ እያወራን እኛ ግድፈት የሞላበት ታሪክ እየሰራን መሆናችን ማወቅ ኣቅቶናል። ኣገራችን ለመጀመርያ ግዜ ወደብ ኣልባ ሁናለች (የተጀመረው ግን ከዓድዋው ጦርነት ጣልያን መረብ ምላሽ ሲቆጣጠር ነው) ፣ ገበሬዎች ከርስታቸው እየተፈናቀሉ; መሬታቸው ለባእዳን በርካሽ ዋጋ እየተክራየ ይሰቃያሉ፣ መንግስት ህገ መንግስት ተገን ኣድርጎ የፈለገው ያስራል፡ ያሰቃያል፡ ይገድላል፡ ይበትናል ወዘተ፣ ለሱዳን መሬት እየተሸጠ ነው፣ ፍርድ ቤቶች የመንግስት ፓለቲካ መሳርያ ሁነዋል፤ ታዲያ ከዚህ ሁሉ የባሰ ምን ሊመጣብን ነው። ይህን ሁሉ ማገናዘብ ኣቅቶን ለመፍትሄ መተባበር ሰንፈን መጠላለፍ ማንነታችን ኣድርገነዋል።

ትምክህተኝነት ከዛም ጠባብነት እንዲሁም መጠላለፍ ኣሁን ደግሞ ሙስና ኣገሪትዋን እየዶቆሳት ነው። ከጅማሪዎች የነበረች ሃገር። ታሪኳና ባህልዋ እያከሰምን ወደ ታች ዓዘቅት እየከተትናት መሆናችን እና ጸጸቱ ኣብሮን እንደሚቀበር ማወቅ ኣለብን። ከዚህ ውርደት ተስማምተንና ተከባብረን በሰላም መኖር እንዴት ያቅተናል። ጣልያንን ያሸነፉ ኣያቶቻችን እኮ ወድ ህይወታችው ገብረው ነው እንጂ እንደኛ እየተለጣጠፉ ኣልነበሩም።

ሁላችን ማውቅ እና መቀበል ያለብን ኣንድ ድርጅት ብቻው ስልጣን ልይዝበት የሚችል ግዜ ኣብቅተዋል። እስካሁን ድረስ በነበሩት ኣስከፊ የከፋፍለህ ግዛ ስርዓቶች ምክንያት በህዝብ ላይ ነቀርሳ ፈጥረዋል። የይቅርታና የእርቅ ስራ ኣልተሰራም። ሰለዚህ መተማመን የለም። ሙሱናም የሰዎች ራእይ ሁነዋል:: ይህ ለመንቀል የተደራጀ ሃይልና ህግ ያስፈልጋል። ይቻላልም።

ስለዚህ ከዚህ ሁሉ ውጣ-ውረድ ተምረን በህይወታችን መልካም ስራ ሰርተን ለመኖር እንብቃ። ለራሳችን ቃል ገብተን እንነሳ። የሌሎች ተበደልን የሚሉትን ወገኖች ብሶት ለማዳመጥ ትእግስት ይኑረን። ያኔ ነው ተግባብተን ለመስራት የሚቀለን። ከሙሱና ነጻ ሁነንም ገለልተኛ የፍትህ ተቋማት እያስፋፋን ህዝባችንን እያስተባበርን እየተረዳን፣ መልካም ስራ በመስራት ራሳችንን ደስ ኣሰኝተን፣ ሃገራችንን እየረዳን፣ ለተተኪ ትውልድ ገንቢ ባህል እያስተላለፍን፣ ሌሎችም በድህነት ሳይሆን በክብር እንዲያውቁን ማድረግ የምንችለው።

ኣወንታዊ ኣስተዋጽኦ
ኣሁን ተቃዋሚ ድርጅቶችን የሚያጣላቸው ፕሮግራም ወይም ፓሊሲ መኖር ኣልነበረበትም: ከነጻ ምርጫ ስርዓት ጋር ተያይዞ ህዝቡ ሊቀበላቸው ላይችል እኮ ይችላል፣ ግዜው እንዴት እየተለዋወጠ እንዳለ ለምን ኣይረዱም; ቢሆንስ ፍጽማዊ የሆነ ፕሮግራም እኮ የለም ዋናው በሰላም መመካከር እንጂ።

1. በሃገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚ ድርጅቶች ተባብረው ለመስራት በንኡስ ፕሮግራምም ቢሆን መስማማት ኣለባቸው።
2. በውጭ ያሉት ተቃዋሚ ድርጅቶችም የበለጠ ሰፊ ስብስብ መፍጠር ይጠበቅባቸዋል።
3. የሃገር ውስጥና የውጭውን ደግሞ የመንግስት ተንኮል ግምት ውስጥ በማስገባት ግንኙነቱ በዚህ ኣንጻር ሊከናወን ይችላል; ዋናው መተማመን እና ላንድ ኣላማ መቆም ነው።

የተቃዋሚ ድርጅቶች፡ ኣንድነት (USA)፣ ሸንጎ፣ ግንቦት 7፣ ኦነግ፣ ኢህኣፓ፣ መኢሶን ሌሎችም ተባብራችሁ ማእከላይ ኣመራር መስርታችሁ፣ የውጭውን ግፊት መምራት እና በሃገር ውስጥ ላሉት ተቃዋሚዎች የሚገባውን ድጋፍ እና ኣጋር መሆን ነው። ሌላ ኣማራጭ ኣለን የሚል ካለ መልካም። ከኢሳያስ ኣፈወርቂ በኩል የሚደረግ ስልታዊ ትብብር ግን ከጠቀሜታው ጉዳቱ ከመጠን ያለፈ እንደሆነ ያለፍት 40 ኣመታት ተመኩሮ ኣስተምሮናል። የጋራ ማእከላይ ኣመራሩ ከተቀበለው ግን ልንስማማበት እንችላለን።

ልዩነትን ተቻችሎ ሀገር መገንባት
እስካሁን ድረስ እንደታዘብነው እርስ በርሳችን መጠላለፍ፣ ለኢህዓዴግ በጎሳና በዘር እየፈረጅን እኛው ራሳችን በጎሳና በዘር ተሰባስበናል፣ ተበደልን የሚሉት ሳናዳምጣቸው ኣልተበደላችሁም እንድያውም ደልትዋችሃል ብለናቸዋል፣ ብሄራዊ ማንነታችን ያለ ህብረት ሊጎለብት ኣይችልም; ህብረት ደግሞ ኣላከበርንም; ተከተሉን እናውቅላችሃለን በዝተዋል። ሀገር ለመገንባት ልዩነትን ኣቻችሎ መደማመጥ; መከባበር; ለበጎ ስራ መትጋት ይጠበቃል። ሁላችን መሪዎች መሆን ኣንችልም ኣንድ መሪ ግን ማስቀመጥ ኣለብን። ትእግስትና ስብእነት ያስፈልጋል።

ኢህኣዴግ መውደቁ ሲቃረብ የተኪው ህብረት ጎልብቶ መውጣን ደግሞ ኣይታይም፣ እንዲያውም ሻክረዋል። ይህ ኣይነት ሂደት የሶማልያ የኢራቅ የኣፍጋኒስታን የመሳሰሉትን ሁኔታዎች እንዲከሰት በር ከፋች ነውና። ኢህኣዴግ ቢውድቅ ምን የፈጠርነው ኣብሮ የመስራት ባህል ኣለና? ልዮነትን ኣክብሮ መሰረታዊ በሆኑ ኣበይት ሕጎች ኣብሮ የመስራት ጅማሮ ማሳየት ኣለብን። የጓደኝነት ይሉኝታ ኣስወግደን ዘላቂ ሃገራዊ ራኢይ ውስጥ እንሳተፍ።
ታደሰ ገብረስላሰ

የታሪክ ጥናት አብነት -የታሪክ ትምህርት ተግዳሮት

$
0
0

(በካሣሁን ዓለም-አየሁ )
ታሪክ ማጥናት አያሌ ጠቀሜታዎች አሉት ።ታሪክን የምናጠናው በተለያዩ ምክንያቶች ነው ።ለታሪክ ማጥናት የመጀመሪያው አስባብ የአእምሮን እድገት ለመለኮስ ግልጋሎት መዋሉ ነው ።ታሪክ ማዕምራዊ ብስለትን ያነቃል።ሁለተኛው ምክንያት ደሞ፣ ለመልካም ዜግነት መሰረት መጣል ነው ።ሶስትም፣ ምግባራዊ ግዴታዎችን ለመፈፀም በብርቱ ያግዛል።በአራተኛ ደረጃ የሚጠቀሰው የታሪክ ጥናት ዞግ ታሪክ ባህልን ለመገንዘብ የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ነው።በመጨረሻም፣ ታሪክ ለዉጥን ለማገናዘብ አስፈላጊነቱ መጉላቱ ።
አሜሪካዊው የታሪክ ምሁር ዋልተር ማክዱጋል ታሪክን መረዳት ለምን እንደሚጠቅም ባስተነተነበት የምርምር ወረቀት ላይ፣ ሶስት አበይት ምክንያቶችን እንደመደምደሚያ አቅርቧል ፣እንዲህም ይነበባል ። ” የታሪክ ትምህርት የአንድን ሀገር ህዝብ አእምሮአዊ እድገት የሚያነቃቃ፣አስፈላጊ የሆነዉን የዜግነት ድርሻ ለመትግበር የሚያተጋ እና ስነ-ምግባራዊ አገልግሎት እንዲወጡ የሚያዘጋጅ ግዙፍ መሳሪያ ነው ።” ታሪክ የወጣቶችን ሕሊና በምክንያት እንዲመራ የሚገራ ፣የሰው ልጆችን ህይወትና አኗኗር ጥልቀት፣ስፋት፣ክብረት(ሪችነስ) ለማድነቅ የሚያስችል ፣ስለ ሰው ልጅ አሳዛኝ የኑሮ መዋዕል የሚያስገነዝብም ትዉስታ የሚያድል ኃይል ነው።የታሪክ እዉቀት በሌሎችም ስነ- እውቀታት(ዲስፕሊንስ) ለምሳሌ ስነፅሁፍ፣ስነ -ልሳን፣ ስነ-ፍጥረት(ሳይንስ ) ፣ነገረ- መለኮት(ትዎሎጂ ) ፣ስነ- ሰብ(አንትሮፖሎጂ )፣ስነ-ሕብረተ ሰብ(ሶስዮሎጂ ) ፣ስነ -ቅሪት ቁፋሮ(አርኬዎሎጂ )፣ፍልስፍና፣ስነ -ህንፃ(አርኪቴክቸር) ወዘተ መሰረት የሚሆን የሚጣጣም አውድ እንደሚፈጥር ለግንዛቤ ከበቃ ሰንበትበት ብሏል ።ታሪክ የማንኛዉም ዘርፈ- ትምህርት ማዕምራዊ ግብዓት፣የአስተምህሮዎች መሰረት መሆኑን በምርምር የተራቀቁ በሰሎች በአፍም በመፅሃፍም ሲያውጁ ነው ዘመናት የተቆጠሩት ።
አሜሪካዊው የስነ- ትምህርት ተጠባቢ ሊኔ ማንሰንም በበኩሉ ስለ ታሪክ እዉቀት ፋይዳ ሲናገር ፣ “ታሪክ ስላለፉት ሁነቶችና ሰብእናዎች እርባና በማስተማር፣ ከራሳችን ህይወትና አኗኗር ጋር በማዛመድ አስተያይተን ይዞታችንን የምናበለፅግበትን መንገድ ለመቀየስ ያግዛል።ሰዎች በሃላፊው ዘመን የሰሩትን የፈፀሙትን በማወቅ ፣የራሳችንን አኗኗር በሰፊ ማዕቀፍ ዉስጥ እያስተዋልን በመመጪ ዘመን ማድረግ የምንችለዉን እንድንተልም የሚያበቃ የጥበብ አቅል ያድለናል።”ብሎ ያሰምርበታል ።ማንሰን ለትንታኔው ማሳረጊያ ያደረገው አረፍተ -ነገር እጅጉን ቀልብ የሚስብ ነበር ፣ ” ካለ ታሪክ እዉቀት ፣ አለምህ በጣም ትንሽ ናት። ” ያለው የብዙሃኑን ትኩረት ማርኩዋል ።ይህም የታሪክን ትምህርት ሁለንተናዊ ረብ ፣ታሪክ መማር ማጥናት የሚኖረዉን ታላቅ ቁብ ለፅድቅ የሚያበቃ ሆኖ እናገኘዋለን ።

የታሪክ ትምህርት አቀናቃኞች የታሪክን ስነ-ዜጋዊና ምግባራዊ አገልግሎት በተመለከተ እንዳብራሩት ከሆነ፣ የታሪክ ትምህርት ምናልባትም ከማንኛዉም የትምህርት ዘርፍ በበለጠና በላቀ ሁኔታ፣ ሰዎች እንዴት ኃላፊነት የሚሰማቸው ሆነው እንደሚቀረፁ፣እንደምን በህብረተሰቡ ዉስጥ አስተዋፅኦ የሚያበረክቱ ዜጎች ሆነው እንደሚታነፁ ያስተምራል።ለዚህ ነው እውቁ የታሪክ ተመራማሪ ማክዱጋል ታሪክ “በዘመናዊ ስርዓተ – ትምህርት ዉስጥ ያለ/የሚገኝ ሃይማኖት ” ነው እስከማለት ርቆ የሄደው ።

ለግላጋዎቹ ወሬዛዎች በሚኖሩበት ሀገር የተገነቡትን እሴቶች ሲማሩ፣ሁነኛ አምሳሎችን (አይድያልስ) ለመጠበቅና ለማስከበር የተደረጉትን ጦርነቶች ሲረዱ ፣የተለያዩ መሪዎችን ድል አድራጊነትና ሽንፈት ሲያጠኑ የራሳቸው ህብረተሰብ እንዴት እንደተበጀና መልክ እንዳበጀ እንዲሁም የነሱ ሚና በዚህ ዉስጥ ምን እንደሆነ በተሻለ መንገድ ደህና አድርገው ይረዳሉ ፣ይገነዘባሉ ።
የታሪክን እውቀት ግንዛቤ መታጠቅ ፣የታሪክን ውል ማስተዋል ማጥበቅ ወጣቶች ያለፉትን ግለሰቦችና ህብረተሰቦች አሳዛኝ ስህተት የሚማሩበትን አጋጣሚ ሁኔታ ሲያዘጋጅላቸው ፣ተመሳሳይ ስህተቶች እንደገና እንዳይሰሩና እንዳይከሰቱ የሚከላከሉበትን አመቺ ምህዳር ያደላድልላቸዋል።
ከዚህም ባሻገር የታሪክ ግንዛቤ ፣ወጣቶች ከቀደሙት ታላላቅ ሰዎች ዉሎ መንፈስ ተምሳሌት ተዉሰው ትላልቅ ህልሞች እንዲያልሙ ያነቃቃል።ባለፉት ግዙፍ ሰብናዎች ገድል አርአያነት ተገርተውና ተቃኝተው በሕይወታቸው ዉስጥ ድንቅና እፁብ ነገሮችን እንዲከዉኑ ዉስጣዊ ኃይል ለማፍለቅ ያበቃል ያጠረቃል ። የታሪክ ምርምር ሊቁ ማንሰን አክሎም ሲያትት ፣” ወደአለም የሚወስዳቸዉን የሚያደርሳቸውን አስፈላጊ እዉቀት የሚቸራቸው የሊበራል አርቶች እዉቀት ነው ።እናም ታሪክን ማጥናት የብልህ ምርጫ ነው ።” ሲል የታሪክን ትምህርት ንዑድነት ያደመቀበት ቀለም በእማኝነት የፀደቀ ብሂልነትን ተክኖ ዘልቁዋል።
በዚህ ፀሐፊ አገማገም፣ የታሪክ ጥናት ባህልንም ለመረዳት ያለው ጠቀሜታ እጅጉን የጎላ ነው ።የታሪክ እዉቀት ባህልን ለመመርመርና ለመተንተን በቁልፍ መሣሪያነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል ።ጠለቅ ዘለቅ ያለ ታሪካዊ ግንዛቤ ሳይጨብጡ ባህልን ለመግለፅ የሚደረግ ሙከራ “ሳያጣሩ ወሬ፣ ሳይገሉ ጎፈሬ” ይሆናል ትርፉ ።ወደሁዋላ መለስ ብለው ታሪክን ካልዳሰሱ ፣የታሪክ መዛግብትን አገላብጠው ካልከለሱ የተለያዩ ባህሎችን መገንዘብ አዳጋችም አታካችም ነው የሚሆነው ።አንድን ባህል ጠንቅቆ ለማወቅ ከሁሉም የሚልቀው ሁነኛ አቀራረብ ባህሉ የተመሰረትበትን ፣ባህላዊ ገፅታው የተንሰራፋበትን አካባቢ ታሪክ በማጥናት ነው ።ስለ ባህል የሚያጠኑ በሳል ተጠባቢዎች እንደሚያስተምሩን ፣ባህል አጠቃላይ(ጀነራል ) እና ልይ ወይንም ዉሱን(እስፐስፊክ ) ተብሎ የሚደለደል ሲሆን ፣ሁለቱንም ባህላዊ ምዳቤዎች በቅጡ ለመረዳት የታሪክ እዉቀት እገዛ በፍጡነ-ረድኤትነት የሚስተዋል ሆኖ ይገኛል ።ታሪክ አጠቃላዩን ሃገራዊ ባህል የምናነፅርበት ፣ልይና ዉሱን የሆነዉን ግላዊና አካባቢያዊ ክበበ-ባህል የምናስተዉልበት መነፅር ሆኖ ያገለግላል ።እንዲህም ሲሆን ፣ታሪክ ለመልካም ዜግነት እዉንታ መሰረት የሚሆነዉን የራስን ልይና ዉሱን እንዲሁም አካባቢያዊ ባህል ጠንቅቆ ለማወቅ፣ የሀገርን የመንግስትን ስርወ- ታሪክ ልብ በማለት ብሔራዊ (ናሺናል )፣ሃገረ መንግስታዊ (እስቴት )፣እና አካባቢያዊ (ሎካል) ሆነው የፀኑ ሕግጋትን ፣ወጎችን ፣ልማዶችን ፣ግዕዛትን (ኖርምስ )፣ትዉፊቶችን ወዘተ ለመተዋወቅና ለመለማመድ አመቺ ጎዳና ይጠርግልናል።
በሌላም በኩል የታሪክ ጥናት እርባና ከሚገለጥባቸው የአተያይ ዘዌዎች(አንግልስ ) አንዱ ለዉጥን ለመረዳት የሚፈይደው ፋይዳ ገሃድነት ነው ።ለውጥ ከያንዳንዱ እለት ህይወት ማህፀን ዉስጥ የሚፈለቀቅ የሕይወት ዘር ነው ። ለዉጥ የህይወትም ቅመም እንደሆነ የሚያወሱ ሃታትያን በርካታ ናቸው ።የህልዉናን ፍሰት ለማስመር ለዉጥን በቅጡ ማየት፣መመርመርና መፍትሄ መሻት ወይ መላመድ ተፈጥሮአዊ ሕግም ጭምር ነው። ” ታሪክ ራሱን ይደግማል “ሲባል ስንሰማ አድገናል።ኖረናልም ።ታሪክ ራሱን ሲደግም ለማስተዋል የታደልንም በአሀዝ እንገዝፋለን መቼም ።ታሪክን ማጥናት እንዴት ለዉጥን በአግባቡ ማጤንና መወጣት እንደሚገባን ያስተምረናል ።ለዉጥ ሲከሰት ዞር ብሎ ኃላፊዉን ጊዜ መመልከት እጅግ ብልህነት ነው።ለዉጡ በተሸኘው ዘመን የነበረዉን ሁኔታ መፈተሽ፣እኛም ሆነ በቅርብ የምናውቃቸው ወይም ታሪካቸዉን የሰማንላቸው ሰዎች፣ቡድኖችና ሰብአዊ ስብስቦች ፣ማህበረሰቦች ፣ህዝቦች ፣ሀገሮች ወዘተ እንዴት ለዉጡን በማስተናገድ ተሻግረን /ተሻግረው ማለፍ እንደቻልን/እንደቻሉ ልብ የምንልበትን አስተዉሎት ይለግሰናል።ይህንንም አስተዉሎት ለገዛ ራሳችን ህይወት አርአያ ምሳሌ አድርገን ልንገለገል እንችላለን ።ከዚህም በተጨማሪ ፣ታሪክ ለዉጥን በወርደ -ስፉህ(ላርጅ ስኬል ) መልኩ አብራርቶ ለማስተንተን አቅል ይቸራል።ለምሳሌ አንድ ሰው ለምን የኑሮ ዉድነት እንደተከሰተ ፣የኑሮ ዋጋው ንሮ ስለምን ህዝቡን በችግር እንዳባዘተ ለማወቅ ቢሻ ፣ታሪክን ዳግም በመፈተሽ የምጣኔ ሃብታዊዉን ዝቅጠትና ድቀት ገፅታ ሊቃኝ፣መንስኤዎቹንና የስፍነቱን መጠን መርምሮ ሊያገኝ አይሳነዉም።ይህም በታሪክ የተፈሸነ፣በታሪክ ተዳውሮ የተሸመነ ግኝት አሁን ባለንበት ወቅት በቃሪያ ጥፊ እሚያጮለንን ዉጥንቅር ፣እግር ከወርች ቀይዶ አላላውስ ያለልን ዉንክርክር ድንግርግር በወጉ ሊያመላክተን ይበቃል።
ከላይ ለማሳየት እንደተሞከረዉና ሁላችንም እንደምናውቀው የታሪክ ትምህርት እንደው ታሪክን ለማተት ብቻ የሚሰጥ ትምህርት አይደለም ። ታሪክ ብዙ እጅግ ብዙ ነገሮችን ያስተምረናል ።ታሪክ የትውልድን አእምሮ በማንቃት ፣የወጣቱን ሕሊና በቁም ነገር በማጠርቃት ወደ ብስለት ያሥገሰግሰዋል።እርምጃዉን ያፋጥናል ።የታሪክ እዉቀት የመልካም ዜግነት መስረት ፣የዜግነት ግዳጅን በስኬታማ መልኩ ለመወጣት የሚያስችል ፣የግንዛቤ አብነት የሚያድል ሲናዊ ክህሎት ያላብሳል።ከዚህም ተያይዞ ፣ታሪካዊ እዉቀት ያለንበትን ማህበረሰብና ሕብረተ -ሰብ ወግና እድር ፣ትውፊቶችና ግዕዛት፣ፍቁዶችና አይነኬዎች ጠንቅቀን፣ ድረ-ገብ ባህርያት አዳብረን በምግባረ -ሰናይነት ኑባሬያችንን እንድናስመሰክር ኮትኩቶ አሳዳጊያችን ነው ።ወደ ባህላዊው ዳራ ስንዘልቅም፣የታሪክ እዉቀት ባህልን በጥራት በምልዓት ለመገንዘብ አይናችንን በሚከፍትልን የብርሃን ዘሐ ይመሰላል ። ታሪክ ማጥናት በእለት ተዕለት ሕይወታችን፣በዙሪያችን በሚፈጠሩት ለዉጦች መሃል እንዴት መኖር እንደምንችል ፣እንደምን የለዉጡን ማዕበል ዋኝተን እንደምንሻገር የሚያግዘንን ኃይል ያስታጥቀናል።
ታሪክን የሸመገለው ዘመን አስታዋሽ ፣ያልሰለጠነና ሁዋላ ቀር ትዉልድ ትዝታ ቀስቃሽ ብቻ አድርጎ መመልከት በራሱ ካለመሰልጠን የሚመጣ ግድፈት ሆኖ የሚታይ ነው ። ጥበባዊ በረከት ይደርጅለትና በሳሉ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን ፣
“የት ጋ እንደሆን ይታይ የኛ ጥበብ መሰረቱ ፣
የሁዋላው ከሌለ የለም የፊቱ ።
ሳይራመድ በታሪክ ምንጣፍ ፣
ሰው አይደርስም ከዛሬ ደጃፍ።”
ያለው የብዙዎችን ትኩረት የማረከው በዋዛ አይደለም ።ታሪክ የትላንት መሰረታችን ከዛሬ ይዞታችን ተነፃፅሮ፣ ነገያችን በተራዘመ አተያይ ታልሞ፣ ተተልሞ የሚገራበት ወደረኛ የኑባሬ ጉባኤችን ነው እኮ። ታሪክ የምንነታችን ፣የእንዴትነታችን ፣የማንነታችን የከየት ወዴት አሻራችን ነዉና ልናውቀው ልንጠብቀው ይገባል።
ታሪክ ሊከበር ይገባል ።ታሪክ ከምናብ ተፈልቅቆ ፣በግለሰባዊ የፈጠራ ግፊት ብቻ ተጨምቆ የሚነገር ተረት ፣የሚፃፍ የፈጠራ ድርሰት /ወግ አይደለም ።ወይም ቡና በአቦል ተቀድሶ በበረካ እስኪያሰልስ እርስ በርስ የሚተጋተጉበት ተረብና የነገር ጉሸማም አይሆንም ፣ከቶም ቢሆን። ታሪክ አግቦና አገም ጠቀምም አይደለም ።ያለ የነበረን የዘመን ዉሎና አዳር ፍርድ ሳያዛቡ ገልፀው ፣ግራና ቀኝ አይተው ያለአድልዎ በይነው ተንትነው ፣ለመጪው ትዉልድ ቅርስ ማስተላለፍ ነው። ታሪክን ማዛባት ፣የተወናከረ ታሪክ ማስተማር ፣ማስራጨት ማስተጋባት ያስጠይቃል ።ያጠያይቃል።ታሪክንም እንዳይማሩ መከልከል ማገድ፣የታሪክ ትምህርትን ቢጋር ከሥርዓተ ትምህርቱ ደልዞ መፋቅ ፣ከፍተኛ ትምህርት ተቁዋማት፣ዩኒቨርስቲዎች የታሪክ ትምህርት እንዳያስተምሩ በመግለጫና ሰርኩላር ማገድ ሃገርን መግደል መሆኑ ሊጤን ይገባል።ሀገራችን በአያሌ አይ-አዎዎች (ፓርዶክሥስ ) አየታመሰች ነው ።ግብርና -መር የኢንዱስትሪ እድገት ለእዉንታ የሚያበቃ የምጣኔ ሀብት ፖሊሲ መታወቂያ ዉሌ ነው ያለው መንግስት፣ ከትምህርት አይነቶች ማዕድ እርሻና ከብት እርባታዉን አካቶ የሚያቅፈዉን የግብርና ትምህርት ድራሹን ካጠፋ ሰንብቷል ።በዚህም የገበሬው ልጅ ወላጆቹን እንዳቅሙ ሊመክር የሚያስችለው አንዳች እይታ እንዳያጎለምስ ድድር ግርዶሽ ጋርዶበታል፣ትንሽም ቢሆን ምርት ማሳደጊያ ምክርና አስተያየት እንዳይሰነዝር ዕድል ነፍጎታል።የታሪክ ትምህርት ወቅታዊ ተግዳሮትም በመፃኢ እኛነታችን ላይ የሚቆልለው አስከፊ ጫና የትየለሌነቱ ካሁኑ ይታየኛል።በረከት ስምዖን ድርሰት የተለማመደበትንና ፣እስከዛሬም ፈውስ ባላገኘለት የንክነት (ንዩሮሲስ ) ሕማሙ መዳፍ ስር ተጨብጦ፣ ፍርሃትና ጭንቀት ተልትሎ በከታተፈው ፣ እብድ እንደያዘው በሶ በነፋስ ተበታትኖ በተዘራ መንፈስ የጫረዉን “የሁለት ምርጫዎች ወግ” ነው የታሪክ አባሪ የምናደርገው ?ተዋደው ተዛምደው ፣ተፋቅረው ተከባብረው የኖሩትን ህዝቦች በጎሳ ነቀርሳ ልክፍት አናቁሮ በማበላላት ፣ለኢሕአዴግ መንሰራፋት አመቺ መንገድ በክፋት ለመቀየስ፣ የሻቢያው ሰላይ ተስፋዬ ገብረአብ ህዝብን በህዝብ በማያባራ ግጭት ለማፋጀት የፃፈዉን “የቡርቃ ዝምታ” ብቻ ነው ታሪክ ብለን የምናወርሰው ?የኤርትራ ታሪክ ሟቹ መለስ ዜናዊ ደደቢት በረሃ ዉስጥ መሽጎ በፃፈው ብቻ ተወስኖ መቅረት አለበት ?የጅማ አባጅፋርን ቤተ- መዘክር ትተን ነው የአኖሌን ሃውልት የምናስጎበኘው ?መምህር ወልደኪዳን በሚያሳዝን ቅጥፈት የደጎሱትን የተንሻፈፈ ተረት ነው ለልጆቻችን አደራ የምናኖረው ? ታዋቂ ምሁራንንና ተመራማሪዎችን ያፈራው ፣በበርካታ ሺዎች የሚሰሉ አፍሪቃዊ የታሪክ ባለሙያዎችን አሰልጥኖ ወግ ማዕረግ ላለው አላማ ያደረሰው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል ለመዘጋት መቃረቡ ምን ማለት እንደሆነ ለመረዳት ነቢይነትን አይጠይቅም ።እጅግ አሳዛኝ ሁነትነቱ ከማንም የተሰወረ አይደለም ።ሁላችንንም ሊያሳስበን ግን ይገባል። አሁን ነው ስለ ታሪክ ማሠብ ። የዛሬን ቱማታ ብቻ ሳይሆን ነገንም ቆም ብሎ ማሰብ ተገቢ ነው።መንግስት በታሪክ ትምህርት ላይ የተከሰተዉን ችግር አስተዉሎ አሰብ እንዲያደርግ ጊዜው ትልቅ ጥያቄ ደቅኖበታል።እንዴት እንደሚዳኘው ከርመን እናየዋለን ።የነገ ሰው ይበለን ።

ጀግንነት የሁለት ፊደላት ፍጥረት ነው ። ሥራ!

$
0
0

(ልክ የዛሬ ወር ነበር ረ/አውሮፕላን አብራሪ ሀይለመድህን አበራ ሲዊዘርላንድ – ጄኔባ ላይ የሠራው – ጀግንነትን)

ሥርጉተ ሥላሴ (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

ዕለተ ሰኞ 17.03.2014 ብሄራዊ ቀኔ ቅኔዬም ነው – ለሥርጉተ። ነገ ደግሞ በብሄራዊ ደረጃ እንዲከበር ይሠራበታል። የነፃነት ቀን በአዬር መንገዳችን ልዩ ምልክት ይሆናል። ከሥራ የተፈጠረው ጀግንነት መጠነ ሰፊ አክባሪም በቂ አድማጭም አለው። በጣም በእርግጠኝነት። ቀለሙ ሰንደቁ ነውና። ረዳት አውሮፕላን አብራሪ ሀይለመድህን አበራ ተገኘ የፈጸመው ተግባር በእግረመንገድ የተከወነ ሳይሆን በውስጡ ባለው ፈቃደ እግዚአብሄር ነው። ገሃዱ ይህ ነው።
(„የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል። እግዚአብሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል። ምሳሌ ምዕራፍ 16 ቁጥር 9)
ወጣቱ ሀይለመድህን አበራ ውስጡ የተሰማውን ጥልቅ ስሜት በሰለጠነ ህሊና ገለጸ። ይህ ደግሞ ክህሎት ነው። ስሜት ለሰጠው እውነት ለመገዛት ወስኖ ፈጣን ምላሽ ሰጠ። የገለጸውም ለሰላማዊ የነፃነት ትግል ትርጉም በሚሰጥ ሁኔታ ነበር። ከዚህ በኋላ ነው ቴክኒካል ነገሮችን ማዬት የሚቻለው። ያስተዋለውን እውነታ ከምክንያታዊ ጭብጦች ጋር አጋብቶ አበለጸገው። ስለሆነም ክህሎቶ በሥነ – ጥበብ ቁመትና ወርድ መለካት አለበት እላለሁ እኔው ሥርጉተ ሥላሴ። በሊቀ -ሊቃውንታት ዓይንም ሊዳሰስ ይገባዋል ባይም ነኝ። የበራ አፈፃፀሙ በራስ የመተማመን ጉልበቱ ነበርና። ረዳት አውሮፕላን አብራሪ ሀይለመድህን አበራ የተነሳው ከገሃዱ አለም ማዕከላዊ ጭብጥና ከነባራዊ ሁኔታውም ነው። በዚህ ሂደት የብዙኃኑ ስሜትና ፍላጎት በአኃቲነት በውህደት ተጋብተዋል።
ሙያ በሥልጠና የሚገኝ ቢሆንም አገልግሎቱ ለህዝብ ስሜት ቅርብ ሲሆንና ማደማጥ ሲችል፤ የሙያው ክህሎት ሆነ ብቃቱ ውስጥን ገላጭ ስለሚሆን ውጤቱን ዓይነ – ገብ ያደርገዋል። ወጣት ሀይለመድህን አበራ እሱ ራሱ የገህዱ ዓለም ታዳሚ በመሆኑ ቅርበቱን የበለጠ ጉልህ ስለሚያደርገው እርምጃው የለማ ትራስ ሆነ ድልዳል አለው። በሥልጠና ያገኘው የክብር ስያሜም ከተግባር ሥራው ጋር ሆኖ ቋሚ ትምህርት ቤት ሊሆን መቻሉ በቂ አድናቂና ቋሚ የድርጊቱ አድማጭ እንዲያገኝ ጉልበት ሆኖታል።
ስሜቱን ኮርኩሮ ለዚህ የላቀ ተግባር ያበቃው ሚስጢር አዳራን ከብዙኃን ውክል ስሜት ጋር ሚዛን ላይ አስቀምጦ የደፋውን እርምጃ የችሎቱን ድምጽ መውሰዱ ነው። ዬሚመጣውን ማናቸውንም መስዋዕትነት አዝናንቶ ለማስተናገድ የቆረጠው የህሊናውን አድማጭነት፤ እንዲሁም ከወገኖቹ የሚያዬውን ብቻ ሳይሆን መሆን የሚችለውን የውስጡን ፍላጎት አድምጦ መወሰን መቻሉና ከዛ ላይም መነሳቱ የአቅሙን ብቃት በጉልህ ያብራራል። የብልህነቱን ጥልቀት ለማዬት አጅግ በርካታ የዝምታ ክንውኖችን ማንሳት ቢቻልም ጸጋውን አውቆ በጥዋቱ ተግባር ላይ ማዋሉ ዘመናትን ሊያሻግር የሚችል ዓምደ ተመክሮ ነው – ለእኔ።
Hailemedhin Abera
ጀግናዬ ሀይለመድህን አበራ ዛሬ በውል ሊታዬን ያልቻለም ሚስጢር በውስጡ እንደ ጸነሰም ለእኔ ይሰማኛል። በጥሞና የመረመረው፤ የገጠመኝ ዘለላዎቹን ሁሉ ንጹህ ጥሬ ሀብቱ እንዲሆኑ አድርጎለታል። ፊድ ባኮቹ ከውጣ ውረዱ ማሳ ያፈሰውን ትልቁና ብቸኛ የወርቅ እንክብል በመሆናቸው „እኔስ? ምን?“ የሚሉትን የህሊና ጥያቄዎች፤ የግራ፣ የቀኝና የማህል ዳኛ፤ እንዲሁም አቃቢ ህግ፤ በተጨማሪም ጠበቃ ሆኖ በሙሉ ልብ ብይን ሰጥቶበታል። የተከደነ ሲሳይ ይሏችኋል ይህ ንጡርነት፤ መረቅነት፤ ክውንነት ነው። ፍላጎቱን ከመንፈሱ ጋር፤ ስሜቱን ከተፈጥሮው ጋር፤ ድርጊቱን ከኃላፊነቱ ጋር አስማምቶ ሙቀት ሸልሞናል። ቅዝቃዜና ብርድ በእሱ የጭምትነት ተልዕኮ የሉም። ጥበቃ አስቀድሞ የደነገገላቸው ተግባራቱ ጥናታዊና ምርምራዊ ናቸው። ፍልስፍናዊና አምክኗዊ ማለትም ይቻላል።
„አሻምን“የገለጸበት መንገዱ ከዚህ በፊት ያልታዩ፤ ፈጽሞም ሊታሰቡ የማይችሉ ክጥፋትና ከትርምስ የዳኑም ናቸው። ይህ „ፍቅር“ የሚባለው የመስዋዕትንት የቆረጠ አርበኛ የሚሻ የኑሮ፤ የህይወት፤ የነፃነት፤ የመብት፤ የብሄራዊ ግዴታ አስኳል ታዬ። አውነታዎች ከሚታዩ ገጠመኞች አውድማ
ለሰንደቅዓላማ፤ ለዳር ደንበር፤ ለህግ የበላይነት፤ ጧሪ ጠዋሪ ላጡ የአደራ ውርስና ቅርሶቻችን ሁሉ ከፍቶ ገብሯል። ወጣቱ ሀይለመድህን አዬር ላይ ሆኖ ከአንዱ ገጸ ባህሪ ወደ ሌላው ገጸባህሪ ሲሸጋገር በቁጥብነት፤ በድንበር፤ ልኩን ለክቶ ሊገለጽ በማይችል ርጋታና በስክነት፤ ሥራን ከግድፈት በብልህንት ነጻ በማውጣት ጀግንነትን ነፍስ ዘራበት። ላላጣጠመው የወጣትንት ቀንበጥ ህይወት መራራን ጽዋ በፍጥነት ቀድሞ እራሱን ሰጠበት። ከምንም ነገር ጋር ንክኪ የሌለው „ፍቅር“ ማለት ይህ ነው።
እኛ አብዛኞቻችን የተሳነን ደግሞ ይህን ማድረግ ይመስለኛል። የምንፈልገውን ሆነ የምንወደውን ነገር እራሱ በቅጡ የማወቅም ተዛነፍ ዕያታ ነው ያለን። ፍላጎታችንም በነፍሳችን ውስጥ ተጠላይ ነው ወይንም ጭሰኛ። አብዛኛውን ጊዜ ጥግና ሳቢያ መፈለግ። ይህም ማለት እኔን የሚኮለኩሉ ጉዳዮች በመጡ ቁጥር ወይ ኮማ ውስጥ መሆን ወይንም ኩብለላ ያሰኘኛል። በዬፌርማታው መሽሎክ። ስለሆነም ፍላጎት ሲባዝን፤ ወይንም ሳይረጋ ወይንም አፈር ሳይለብስ ክው ብሎ ደርቆ በኖ ይቀራል። ፍርፋሪና እንጥፍጣፊ የተሰናበተበት ምኞት። ምክንያቱም ቋሚ ፍላጎትን በውስጥ የማነፅ፤ በጽናት አበክሮ የማበቀል ብቃቱ ውሽልሽል ስለሚሆንም ነው። ልጅም፣ ታናሽም የሆነው የትናንት አንድ ፍሬ „ሥራ“ በአጽህኖትና በተደሞ የሰበከው ይህንኑ የውስጥ ግድፈታችን እንድናርም ነው። አንድ ፍጥረት የ30 ዓመት ወጣት ትንፋሽን ሳቢና ጉልበታም አቅም ኖሮት እንዲህ የዓለም አጀንዳና ፊኖሚና ለመሆን በቃ። በቃ! ያበቀለው የሥነ – ህይወት ዋርካ። እራሱን ለፍላጎቱ የማስገዛት ጥንካሬውም አይነታ ብሂል ነው የመሆን አንጎል።

ገና በጋሜነት በኩብልና፤ እጅግ በሚያሳሳው አፍላነት ዕድሜው ለተሰጠው ጸጋ ራሱን የሚያስገዛ ፍጡር ፍላጎቱና አሱ ህይወትን በፍጥነት መረዳቱ ብቻ ሳይሆን፤ በጥልቀት የማጤን፤ ስለነገ ብቁ ግንዛቤ የመኖር ብሩህ ህሊና ላላቸው ፤ እንደ ረዳት አውሮፕላን አብራሪ ሀይለመድህን አበራ ተገኘ ላሉ ብቻ የተሰጠ መክሊት ነው። ድርጊቱ ከገሃዱ ዓለም ጭብጥ ገዝፎ የወጣ በመሆኑ ጥልቅ ተግባሩ ጀግና ሊያሰኘው መቻሉ ቢያንሰው እንጂ የሚበዛበት ሊሆን ከቶም አይገባም። ድምጽን በዳጣ አንባገነን ለተገፋ ብዙሃን ህዝብ ለዘመኑ ፍትህ ርትህም ነው። በዚህ ሥም ነገ ሚሊዮኖች ይጠሩበታል። ታሽቶና ነጥሮ የወጣው ተግባሩ ውበቱ ያለው ከእውነታው ማዕከል በመሆኑ ፈተናን የመርታት አቅሙም የዚያኑ ያህል ጉልበታም እንደሚሆን ባለሙሉ ተስፋ ነኝ።

ህይወት ወይንም መኖር ሲባል በማህበረሰቡ የሕይወት ውጣ ውረድ ውስጥ በንቃትና በባለቤትነት ስሜት መሳተፍ ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ አንዲህ ላቅ ብሎ ለተሰጣቸው ሰዎች የህብረተሰቡ ችግር፣ ሰቆቃ ሆነ መከፋትም ከሌላው የህብረትሰብ ክፍል ይልቅ ቀድሞ ያሳስባቸዋል – ይታያቸዋልም። ለዚህም ነው መግቢያ ላይ ሥራው በሥነ – ጥበብ ዓይን ሊታይ ይገባዋል ያልኩት። ስለሆነም ሃይላችን የህዝባችን የመንፈስ ውጥረታዊ ፍርሃት፤ ዬየጓዳው ጃንቦ ስጋት፤ የተስፋ ድርቀት፤ ዬህልም ርቀትን በጥንቃቄ በማስተዋል፤ መቼቱንም አዋቅሮ ለራሱ ሳይሰስት፤ ግጭቶችንም በማስማማት ለወቅቱ ዬተፈቀደለትን የሙሴነት ተስጥዖ ሳያልፈው ወይንም ሳይዘለው ወይንም ሳያፍነው በመሆን በዝምታ ድባብ ቀደሰው። ስለዚህ ለእኔ ከጀግንነትም አልፎ የህይወቴ ነው ማህደሬም።
ወጣት ሀይለመድህን የህውከት ጦሮ የሚንጠውን አዬር ራሱ ነፃ አውጥቶታል። ማህል ላይ የተገተሩ ዥንጉርጉር፤ ስርክራኪ፤ ሸውራር ተዛነፍ ፍላጎቶችን ሁሉ በዝምታ በማረቅ፤ መስመራቸውን በፍጥነት እንዲያስተካክሉ በማድረግ የኃይል አሰላለፉን እንደ ገና ሪባይዝ በማደረግ ጥንቃቄና ጥራትን አውጆለታል። እንዲሁም ካለገላጋይ ከቁንጨጮ ላይ ወጥቶ የሚያተራምሰውን የግል ኢጎም ዘቅዝቆ አንጠልጥሎታል። ለሌላው መኖር – ክብርም ለህዝብ ፍላጎት መቅድምነት በማለት ወጤታማ ተግባር ከውኗል። ስለሆነም ጀግናዬ ሀይለመድህን አቅምን ሳያባክን የአደራን ጥሪ „እሺ“ ብሎ ስለፈቀደ እንሆ ተወደደ።

እንደ መቋጫ – „ጀግናችን አጀንዳችን“ ብዬ በጻፍኩት ላይ „አመላችሁ ነው። የሰሞናት ነው፤ የወረት ነው“ የሚል አስተያዬት ከአንድ የጹሑፌ ታዳሚ አንብቢያለሁ። የተከበሩ የሀገሬ ልጅ ጹሑፌን ጊዜ ወስደው ስላነበቡልኝ ከፍ ያለ ክብር አለኝ። አመሰግነወትምአለሁ። ልነግረውት የምሻው ቁምነገር ግን አለኝ። ያዳምጡኝ። ሥርጉተ ሲዊዘርላንድ እያለች የማነን ጎፈሬ ታበጥር ይመስለወታል? ሥራዬ ምን ሆነና?! „ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት“ መደበኛ የህይወቴ አጀንዳዎች ናቸው። ጠረኖቼ ትንፋሾቼም መሆኑንም ልግለጽልዎት እሻለሁ። በጣም በእርግጠኝነት ልነግረዎት የምሻው ለእኔ ወጣት ሀይለመድህን መስቀሌ መሆኑን ነው — ተግባባን ወዳጄ።
ከሚያዚያ 10 ቀን 2014 ጀምሮ ደግሞ በቅኔው ንጉሥ በጸጋዬ ድምጽ ራዲዮ ፕሮግራሜ በዬ15 ቀኑ ቋሚ ዓምድ ይኖረዋል „የተስፋ ማህጸን“ www.lora.ch.tsegaye. ይጠብቁኝ። ግን እርሰዎ „የኢትዮጵያ ምድር ጦር፤ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል፤ የኢትዮጵያ አዬር ኃይል፤ ኢትዮጵያን ያስቀደሙ የሲቢክስ ማህበራት፤ ድርጅቶች ሁሉ በነቂስ እዬተለቀሙ ወያኔ በዱድማ ህሊናው ሲንዳቸው ከቶ የት ነበሩ?!“ የአንጋፋው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ሙሴ ሰማዕት አሰፋ ማሩ በጠራራ ጸሐይ በባሩድ ሲንድ —- በደል አይረሳም ያገረሻል እሺ። ይበሉ እንደ አውሮፓውያኑ ሰዓት አቆጣጠር ከ15 እስከ 16 ሰዓት ሚያዚያ 10.2014 አዬር ላይ እንገናኝ። ለሚመድቡልኝ ጊዜም በቅኑ መንፈስ የቅድሚያ ምስጋና ተላከ – ለእርሰዎ- ለጌታው።

ውዶቼ የእኔዎቹ ብትክትኮች፤ አፋፍ ላይ የተንጠለጠሉ፤ ማጣፊያ ያጠራቸው፤ እንደሚሉን ሳንሆን እንደ ፍላጎታችን ጠንካሮች እንሁን። ቀዳዳውን ሁሉ የምናሸፍንበት ዘመን መሆን አለበት። በተለይም ሴቶች፤ እሺ ልዕልቶቼ። ክብረቶቼ የሀገሬ ልጆች ዛሬ በአጭር ትጥቅ ዕይታዬን አጋርቼ ሽው ልል ነው …. የጀግንነት የአንደኛ ወሩ „የተስፋ ማህጸን“ ዝክረ ሀይለመድህን በዚህ መልክ ማህሌት ተቆመለት። ሙሉቀን ከድንግል እግር ሻማ ይበራል። ወገኖቼም ፌስቡካችሁን ቲውተር አካውንታችሁ በጀግናቹሁ አንቆጥቁጡት። ፈቅዳችሁ ለሰጠችሁኝ ጊዜ አከበርኳችሁ። ወደድኳችሁም። መልካም የተግባር ጊዜ – ለሁላችንም። ሥራችን – እንሥራ!

እግዚአብሄር ስለሚሰጠን የመንፈስ ማረፊያ ጀግና አድናቆታችን ለዘለአለም ነው!
ፈተናን ከመፈጠሩ በፊት አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር ኢትዮጵያዊነት ብቻ ነው!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

በነፃነት ቀን ነፃነት ማጣት !

$
0
0

ከይድነቃቸው ከበደ

ሰብአዊ መብቶች እያንዳንዳችን ሰው በመሆናችን ብቻ የሚገቡን ከሰብአዊነታችን ተለይተው ሊታዩ የማያችሉ መብቶች ናቸው፡፡ መንግስታት እነዚህን በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና የተሰጣቸውን ሰብአዊ መብቶች ለማክበር ለማስከበርና ለማሟላት በቀዳሚነት ኃላፊነት አለባቸው፡፡ በዚህም መሰረት ኃላፊነት ከፈረሙ ቀደምት አገራት መካከል ኢትዩጵያ ትገኝበታላች፡፡
ይሁን እንጂ የሴቶች ሰብአዊ መብቶች በሚፈለገው መልኩ ተግባራዊ ካለመሆኑ ባሻገር ኢ-ፍትሃዊነት እጅግ የበዛ ነው፡፡ ይህም በመሆኑም እ.ኤ.አ. በ1908 በአሜሪካ ኒወርክ ከተማ በጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ይሰሩ የነበሩ ላብአደር ሴቶች ‹‹ለእኩል ሥራ እኩል ክፍያና የተመቻቸ የሥራ ሰዓት ለሴቶች›› በሚል መፈክር የሥራ ማቆም አድማ በማካሄድ የሴቶች ድምፅ እንዲስተጋባ አድርገዋል፡፡ ይህን ተከትሎ የዓለም ሴቶች በማህበር በመደራጀት ትግላቸውን በማጠናከራቸው የዓለም መንግስታትን አስተሳሰብ በመለወጥ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባል አገሮች የሴቶች መብት ስምምነት/ኮንቪክሽን/ እንዲፈራረሙ እብይ ምክንያት ሆነዋል፡፡
New Picture (17)
እ.ኤ.አ. በ1910 በኮፕን አገር ከተማ በተደረገው ሁለተኛው ዓለም አቀፍ የሴቶች ጉባሄ ላይ የመነሻ ሃሳብ በማቅረብ ማርች 8 በየዓመቱ እንዲከበር ያደረጉት ሴቶች ለመብታቸው ያደረጉትን አስታውጾ ለመዘከር ዓለም አቀፍ መድረክ ለማመቻቸት በመቻላቸው ስማቸው በአክብሮት ይነሳል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓሉን ያከበሩት ጀርመን፣አውስትራሊያ፣ሲውዘርላንድ እና ዴንማርክ ለመሆናቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ከዚሁ የአንድነት ተምሳሌትነት በመነሳት በዓለማ አቀፍ ደረጃ ማርች 8 የሴቶች ቀን በማድረግ ዓለም አቀፍ ስያሜዎችን በመስጠት አገራችን ኢትዮጵያ ጨምሮ በተለያየ መልክ ሲከበር አመታትን እቆጥሯል፡፡ የዘንድሮዉም ማርች 8 አለም አቀፍ የሴቶች ቀን እስከ ዛሬ በአገራችን በተከታታይ የኢትዮጵያ ሴቶች ካከበሩት በዓላት የሚለየው ሁሌም የምኮራባቸው የሰማያዊ ፓርቲ ሠላማዊ ታጋይ ሴቶች የፈፀሙት ገድል ነው፡፡
በአገራችን ኢትዮጵያ የዜጎች መብት በእኩልነት ተጠብቆ በሴቶች ላይ አጥልቶ የኖረው የጾታ ጭቆና እስከዛሬ ምላሽ ያላገኘ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡በተለይ በወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት የስልጣን ዘመን የሴቶች ጭቆና እና የመብት እረገጣ በህግ ማቀፍ ውስጥ መሆኑ ይብልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡ ይህን ለማለት የሚያስደፍረው የህጎች ሁሉ የበላይ ህግ ነው በሚባለው ህገመንግሰት የፆታን አድልዎ የሚቀርፍ እና የሴቶችን መብት የሚያመላክት ድንጋጌዎች በውስጡ አካቶ የያዘ ቢሆንም ተግባሪዊነቱ ፕ/ር መስፍን እንዳሉት ‹‹የተፃፈበትን ወረቀት ያህል ዋጋ የማያወጣ ነው››፡፡ ዋጋ አለው እንኳን ከተባለ የትርፉ ተካፋይ የሆኑት የገዥው መንግሰት አጨብጫቢዎች እና የጡት ልጆች ብቻ ናቸው፡፡
በአገራችን መከበር ከጀመረ ከሦት አስርታት በላይ ያስቆጠረው ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለሴቶች በሴትነታቸው ከሚደርስባቸው ጾታዊ በደል እና የሰብአዊ መብት ጥሰት ያስቀረላቸው አንድም ነገር የለም፡፡ በተለይ ከላይ እንደተገለፀው በወያኔ/ኢህአዴግ መንግሰት ሴቶች በህግ እና በመብት ጥላ ስር ከፍተኛ የሰብአዊና የዲሞክራሲ ጥሰት እየተፈፀመባቸው ይገኛል፡፡
እጅግ አስገራሚው ክስተት ደግሞ የኢህአዲግ ሴቶች ሊግ ፣ የሴቶች ፎረም ኢህአዲግ የሚያዘው እና አገዛዙ ያስተባበራቸው በርካታ የሴት ማህበራት ተጠሪነታቸው በቀጥታ ለወያኔ መንግስት ስርአት ነው፡፡ ስርአቱ ደግሞ የመላው ኢትዮጵያዊያን ድጋፍ እና ይሁንታ ያላገኘ መሆኑ ነው፡፡ ነገሩን ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርገው ደግሞ ኢትዮጵያዊያን ሴቶች ከመንግስት ድጋፍ ውጪ በራሳቸው ፍቃድና አቅም አንድም የተደራጀ ማህብር የሌላቸው መሆኑ ነው፡፡ እርግጥ ነው የሴቶች የፅዋ እና የእድር እንዲሁም የዕቁብ ማህበራት በአገራችን ለቁጥር የሚታክቱ ነው፤ግን እነዚህ ማህበራት የሴቶችን ሁለንተናዊ ችግሮችን የሚቀርፉ አይደለም፡፡
ለመደራጀት ሳይሆን ለማደራጀት ትኩረት እና ድጋፍ የሚሰጠው መንግሰት በሴቶች ላይ ማላገጥን ስራዬ ብሎ ተያይዞታል፡፡ለዚህም እንደማሳያ ከታችኛው የቀበሌ ባለስልጣን ጀምሮ እስከላይኛው የአገር መሪ የሴቶች እኩልነት እና የመደራጀት መብት በህግ የተጠበቀ እንደሆነ ሳይታክቱ የሚገልፁት ነገር ነው፡፡ይሁን እንጂ የሴቶች እኩልነት እና የመደራጀት መብት ለኢህአዴግ አባልነት እና ቤት ለቤት ቡና እያጣጡ የተነገራቸው መልሰው ከማውራት ከቅያስ ወይም ከጎሮ ከድሬነት ያለፍ ተሳትፎ ከተደራጁበት ሳይሆን ከደራጃቸው አካል ያተረፉት ነገር የለም፡፡ ከላይ የተጠቀሰው አሳብ ለመረዳት እና ለመታዘብ ብዙ መራቅ አያስፈልግም በህገመንግስቱ መሰረት ተደራጅተዋል የተባሉ ማናቸውም እንዲሁም በየትኛውም ቦታ የሚገኙ የሴት ማህበራት ከመንግሰት ተፅኖ ውጪ ላለመሆናቸው ከማህበራቸው የስም አወጣጥ ጀምሮ ተግባራቸው በመመልከት በቀላሉ ማህበሩ እና ማህበርተኞችን እነማን እንደሆኑ ለመረዳት ይቻላል፡፡
ለዚህ ፁሑፍ መነሻ የሆነው አሳብ ዘንድሮ ተከብሮ ሳይሆን ተደፍሮ ለማለት በሚያስችል ሁኔታ ማርች 8 መሰረት ያደረግ ነው፡፡ እንደሚታወቀው የባለፈው እሁድ ማርች 8 አስመልክቶ የሴቶች 5 ሺህ ኪ.ሜ ሩጫ ውድድር ተካሂዶአል፡፡ በውድድሩ ላይ ቁጥራቸው የበዛ ሴቶች ተሳትፈዋል ፤ከተሳታፊዎቹ ብዛት ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ በአነስተኛ እና ጥቃቅን መንግስት ያደራጃቸው ሴቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ሴቶች አደባባይ ይዘው የወጡት አሳብ ጥቃቅን መሆኑ በእርግጥም ማህበርተኞቹ ምን ያህል አንድ ለአምስት ‹‹እደተጠረነፉ›› የሚያሳይ ነው፡፡ የጉዳዩ አሳሳቢነት የሚጀምረው እነኚህ ጢቂት ‹‹የተጠረነፉ›› ሴቶች በነፃነት ቀናቸው ነፃነት የተነፈጋቸው መሆኑ ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ እሩጫው ላይ የተሳተፉት በራሳቸው ፍቃድ ሳይሆን በድረጅታቸው ትዕዛዝ ነው ሊያስብል የሚያስችል የተለያየ ‹‹ልማታዊ›› የሆነ መፈክሮችን ሲያሰሙ ተደምጠዋል፡፡በመንግሰት ልዩ ድጋፋ የተደረገላቸው እነኚህ ሴቶች ለሚደግፉት ሳይሆን ለተገደዱበት ዓላማ የመሰላቸውን መፈክር እና ቀረርቶ በማሰማት እንዲሁም የተለያዩ ፖስተሮችን በመያዝ በዕለቱ ሲንቀሳቀሱ ታይተዋል፡፡
ይሁን እንጂ ለመንግስት ደጋፊዎች የተፈቀደው ለሌሎች ለመንግሰት ተቃዎሚ ሴቶች ፖሊስ ያደረገው ክልከላ እና እስራት ክስተቱን አስገራሚ ብቻ ሳይሆን አሳሳቢያ ደርገዋል፡፡ እንደሚታወቀው ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ነው፤ ይህ ቀን ሴቶች ተሰባስበው ከበሮ ይዘው የሚደልቁበት ቀን ሳይሆን ለነፃነታቸው ቀደምት ሴቶች ያደረጉትን ተጋድሎ በመዘከር ያሁኖቹ ሴቶች ለበለጠ እኩልነት እና ነፃነት በጋራ የሚቆሙበት የቃል ኪዳን ቀን ነው፡፡ ይህም እንደሆነ የተረዱ ሴቶች በነፃነት ቀናቸው ስለነፃነታቸው ከፍ ባለ ድምፅ ሲዘምሩ ማየት ምንኛ መታደል ነው ! ይህን በድፍረት ላደረጉት የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶች አድናቆት ሊቸራቸው እና ድጋፍ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ሴቶች በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ በአደባባይ ታፍሰው ለእስር የበቁት በእኔ ዘመን ይህ የመጀመሪያ ነው ፡፡የኔ ዘመን ደግሞ 23 ዓመት ሙሉ የሴቶች የፖለቲካ ተሳትፎ የበላው ጅብ አልጮው ብሎ ተቸግረን የከረምንበት ወቅት ነው፡፡ እርግጥ ነው ይህ የሆነበት ምክንያት ለማወቅ እና ለመዘርዘር ሰፊ ጥናት ያስፈልጋል፡፡ የችግሩ አሳሳቢነት እንደተጠበቀ ሆኖ እንቢ ለነፃነቴ በማላት አደባባይ በመውጣት የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶች ‹‹ እኔ የጣይቱ ልጅ ነኝ ! እስክንድር ይፈታ ! እርዮት ትፈታ ! አብበከር ይፈታ ! አንዱአለም ይፈታ ! መብራት እና ውሃ ናፈቀን ! ፍትህ እንፈልጋለን ! ›› እና የመሳሰሉትን መፈክር በልበ ሙሉነት በማሰማት ያሳዩት ቆራጥነት ታሪክ መቼም የሚዘነጋው አይደለም፡፡ በይበልጥ ደግም በዚሁ የፖለቲካ አመለካከታቸው ምክንያት ብቻ ለእስር መዳረጋቸው የመንግስት ስርዓት ምን ያህል አምባገነን እና ጨቋኝ እንደሆን በግልፅ የሚያሳይ ነው፡፡

የቁልቁለት መንገድ! – ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

$
0
0

በማስመሰል ታጥሮ መሆን በጠፋበት
ምን አገባኝ የሚል በተከማቸበት
የባይተዋር መንፈስ ከሞላ ባገሩ
ዘመኑን ማወቂያ ይሄ ነው ሚስጥሩ
ይሄን ጊዜ ጠርጥር እንደጠፋ ዘሩ፡፡
(ገጣሚ ደምሰው መርሻ/ያልታተመ)
Temesgen Desalgn
አዎን፣ ገጣሚ ደምሰው እንዳለው እኔም በዚህ ዘመን “ዘሩ እንደጠፋ” አሊያም ሊጠፋ እንደተቃረበ እጠረጥራለሁ፡፡
ስለምን? ቢሉ …በኢትዮጵያችን ለህሊናው፣ ለሕዝብና ለሀገሩ የሚቆረቆር፣ የእውነት ተሟጋችና የሞራል ልዕልናን የተቀዳጀ ሙሉ ሰው ፈልጎ ማግኘት እጅግ አተካች ሆኗልና፡፡ የግል ጥቅም አሳዳጅ፣ አፋሽ-አጎንባሽ በሞላበት፣ እንደ ቴዎድሮስ ለሀገር ቤዛ መሆን፤ እንደ ግርማሜዎቹ እና ወርቅነህ የራስን ምቾት ወዲያ ጥሎ በጠገበ ሆድ ከወገን ጋር መራብና ከጎኑ መቆም፤ እንደ አቶ ሽፈራው ደሳለኝ አስፈሪ ሞት ከከበበው ሸለቆ ውስጥ በህይወት ለመውጣት ሲባል የጠላትን ጫማ ከመላስና ያላመኑበትን ተናግሮ ምህረት ከመጠየቅ ይልቅ በድፍረት ሞትን ፊት ለፊት መጋፈጥ ወይም ግንባርን ለአረር መስጠት እንደ ተረታ-ተረት ከተቆጠረ ዘመናት አልፏል (አቶ ሽፈራው ደሳለኝ ማን ናቸው? ለሚለኝ አንባቢዬ ‹‹የታኀሣሡ ግርግር እና መዘዙ›› የተሰኘውን የብርሃኑ አስረስ መጽሐፍ ገፅ 302ን እንዲያነብ እጋብዘዋለሁ) አሊያም ደግሞ የሰው ዘር በመሆን ብቻ የሚገኘውን የሞራል ልዕልና ከትውልድና ሀገር ጥቅም አኳያ ለማጠየቅ በዚህ አውድ ለማነሳው ተጠየቅ በአንፅሮ ለማፍታታት ይጠቅመኝ ዘንድ እኔው ራሴ እዚሁ ጠቅሼው አልፋለሁ፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ‹‹በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጊዜ የድጋፍ ንግግር አድርጋችኋል በማለት በመንግስት ተይዘው ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ከተላኩት አንዱ የሆኑት…›› ብለው ከአቶ ሽፈራው ደሳለኝ ጋር ከአስተዋወቁን በኋላ እንዲህ በማለት ትርክታቸውን ይቀጥላሉ፡- ‹‹…አቶ ሽፈራው ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ተልከው ለፖሊስ ቃላቸውን ሰጥተው ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ የእምነት ክህደት ቃል ሲጠየቁ ዳኛው ‹ሠርተሃል ለተባለው ወንጀል ጥፋተኛ ነህ፣ አይደለህም?› ይላቸዋል፡፡ ‹የቱን ወንጀል?› ሲሉ አቶ ሽፈራው ዳኛውን ይጠይቃሉ፡፡ ዳኛው አቶ ሽፈራው ሠርተዋል የተባለውን የወንጀል ቃል ሊናገሩት አልወደዱም አልደፈሩምምና ‹አንተ የሠራኸውን?› ብለው ጠየቁ፡፡ አቶ ሽፈራው ‹እስቲ ወንጀል የተባለው ይነበብልኝ› ብለው አጥብቀው ይጠይቃሉ፡፡ ይሄን ጊዜ ዳኛው ሳይወዱ ‹ይህን ጣሳ እግዚአብሔር ገላገለን፣ አወረደልን ማለትህን፤ …ለዚህ ጥፋተኛ ነህ አይደለህም?› ይሏቸዋል፡፡ ‹የለም ተስተካክሎ ይጻፍልኝና እምነት ክህደቴን ልናገር› ይላሉ፡፡ ‹የለም በዚህ ላይ ጥፋተኛ ነኝ በል› ይሏቸዋል፡፡ ‹ትክክለኛ ቃሌ ይጻፍና ነው እንጂ እንዲሁ ጥፋተኛ ነኝ፤ አይደለሁም፤ አልልም› ብለው ይመልሳሉ፡፡ ‹እሺ ምን ተብሎ ይስተካከል› ሲሏቸው፤ ‹ይህን የበሰበሰ የተጠረማመሰ አሮጌ ጣሳ እግዚአብሔር ገላገለን ነው ያልኩት› ሲሉ ዳኞቹ የተባለውን አልሰማንም ለማለት ራሳቸውን ጠረጴዛ ስር አግብተው ተደበቁ፡፡››
በዚህ ዘመን ራሳቸውን ጠረጴዛ ስር አግብተው እንደ ሰጎን አንገታቸውን ቀብረው በፍርሃት የሚኖሩ አድር፣ እበላ-ባይ፣ ፈሪ ሰዎች የአቶ ሽፈራውን ባመኑበት መቆም እንደ አጎል ጀብደኝነትና ሞኝነት ቢቆጥሩት አስገራሚ አይሆንም፡፡ የሆነው ሆኖ እንደ ብልህነት አሊያም ብልጥነት ተደርጎ የሚወሰደውን የአድርባይነት ‹‹ስልት›› ለማሳየት አንዲት ሀገርኛ ምሳሌ እዚህ ጋ ለንፅፅር ላቅርብና እንደ ፕሮፌሰር መስፍን ለራሴ ጽሑፍ ‹‹F›› ከመስጠቴ በፊት ወደ አጀንዳዬ ልዝለቅ፡፡
ታሪኩ ዝናው በስፋት የናኘ ሽፍታ የመሸገበትን (ግዛቱ ያደረገ) ጥቅጥቅ ያለ ጫካ አቋርጦ ስለሚያልፍ መንገደኛ ገጠመኝ ነው፡፡ መንገደኛው ለሰዓታት ከተጓዘ በኋላ ድንገት ሽፍታው እጅ ይወድቅና ስንቅ የቋጠረበትን ስልቻ ጨምሮ ከላይ እስከታች ይበረበራል፤ ሆኖም ሰባራ ሳንቲም ሊያገኝበት ባለመቻሉ ከመጠን በላይ የተበሳጨው አያ ሽፍታ ሆዬ ንዴቱን ለማብረድ ሲል ‹‹ውዳሴ ዜማ አቅርብልኝ!›› በማለት ቀጭን ትዕዛዝ ይሰጠዋል፤ በፍርሃት ነፍሱ እጉሮሮው የተወተፈችበት መንገደኛም ተንፈስ ብሎ ለመረጋጋት እየሞከረ እንዲህ ሲል አቀነቀነለት ይባላል፡-
‹‹አይኑ የተኳለ ጠላት የሚጋረፍ
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ 2
ጠብ-መንጃ ገስጋሽ ጉብታ ተሻግሮ
ከዘብጥ የሚናደፍ
እንደሚካኤል ነህ ጠላትህም አይተርፍ!››
እነሆም የሀገሬ ምድር እንዲህ ባሉ ሀሞተ-ቢስ አወዳሾችና አስመሳዮች ተጥለቅልቃ እጆቿን ወደ ሰማይ ከዘረጋች (ሱባኤ ለመግባት) ሰነበተች፡፡ በርግጥም ከብዙሀኑ በተሻለ ማንሰላሰል ይሳናቸዋል ተብለው የማይታሰቡ ‹‹ምሁራን››ም ሆኑ ‹‹መንፈሳዊ››ነታቸው የበዛ የኃይማኖት መሪዎች በግል ጥቅመኝነት ታውረው ከስርዓቱ ጋር እጅና ጓንት በመሆን የጭቆና አገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም በሀሰት መስካሪነት የቅጥፈት ምላሳቸውን ሲያንበለብሉ መስማት ‹እግዚኦ› የሚያስብል አስደንጋጭ መናፍቅነት መሆኑ ቀርቶ እንደ ተራ ነጋዴ ንግግር፣ ተራ የዕለት ተዕለት አጋጣሚ ከሆነ ዘመናት ተቆጠሩ፡፡ ‹‹መንፈሳዊያን›› አባቶች በተከበረው ቤተ-መቅደስ ምኩራብ ላይ ከመእምናኑ ፊት ለፊት ቆመው ቃየልን ‹‹አቤል››፣ በርባንን ‹‹መሲህ›› በማለት ሲሰብኩም ለአመል እንኳ ድንቅፍ አያደርጋቸውም፤ ከግላዊ ጥቅማቸው አሻግረው የግፉአንን የስቃይ እሮሮ ማድመጥም ሆነ ለሌላው ማሳወቅ ጭራሹንም አይሞክሩትም፡፡ ‹‹ምሁራን›› ተብዬዎቹም አርቲስት ሰለሞን ተካልኝ ‹‹ውበት ከቅንድቡ የሚፈስ›› እንዲል፤ ‹አይኑ የተኳለ› እያሉ በሕፃናት ደም ሳይቀር የጨቀየውን ኢህአዴግ መራሹን መንግስት እንዴት እንዴት ‹ብፁእ› አድርገው የውዳሴ ከበሮ ሲመቱለት እንደሚያድሩ እዚህ ጋ ዘርዝሮ ለማቅረብ ማሰብ አባይን በጭልፋ አጋብቶ ለመጨረስ እንደመሞከር ያለ ዕብደት ያስቆጥራል፡፡
ወጣም ወረደ እንዲህ አይነቱ የሞራል ዝቅጠት በትላንት ወይም በዛሬ የእድሜ ገደብ የሚለካ አለመሆኑን በድፍረት መናገር ይቻላል፤ ምክንያቱም በነገሥታቱ የአገዛዝ ዘመን የጀመረና በጣሊያን የአምስት ዓመቱ የወረራ ወቅት እንደወረርሽኝ የተስፋፋ ስለመሆኑ በቂ ማሳያዎች አሉ፡፡ ይህ እንግዲህ ‹‹ሀገር›› ለተሰኘ ማህተም መስዋዕት የሆኑትን አቡነ ጴጥሮስን የመሳሰሉ ታሪክ በታላቅ አክብሮት የሚዘክራቸውን ቀዳማይ አባቶችና እናቶችን ሳንዘነጋ ነው፡፡ እናም የሩቁን ትተን ከ1983ቱ የመንግስት ለውጥ ወዲህ ያለውን እንኳ ብንመለከት ይህን መሰሉ ክስረት ዙሪያችንን ከቦ ሊውጠን የቀረው ስንዝር ታህል ርቀት ብቻ መሆኑን ለመረዳት የማሕበራዊ ሳይንስ ምሁራን ትንታኔን ማገላበጥ አይጠይቅም፡፡ ያኔ ገና በለውጡ ማግስት ህወሓት እና ሻዕቢያ በአንድ አንቀልባ ካልታዘልን በሚሉበት የ‹‹ጫጉላ›› ዘመን፣ ከኤርትራ ምድር የወርቅ ጥርሳቸው ሳይቀር በጭካኔ ወልቆ ባዶ እጃቸውን የተባረሩ ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ በጉምቱው ምሁር ፕሮፌሰር እንድሪያስ እሸቴ የተመራው አጣሪ ቡድን ‹‹ውሸት ነው! ይህ አይነቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ኤርትራ ይኖሩ
በነበሩ ኢትዮጵያውያን ላይ አልተፈፀመም!!›› በማለት አይኑን በጨው አጥቦ በድፍረት ሲያስተባብል፣ አንጀታችን እያረረ ‹‹ይሁና!›› ብለን በትዝብት ማለፋችን እውነት ቢሆንም፤ የዝምታችን ውስጠ-መልዕክት ያልገባው ፕሮፌሰሩ ግን ያረረው አንጀታችን ይበልጥ እርር ይል ዘንድ በተለመደው ቅጥፈቱ ታላቁ የዐድዋ ድል ባለቤትነትን ከሀገር ከፍታ፣ ቁልቁል ወደ ጎጥ ለማውረድ ያልፈነቀለው ቋጥኝ፣ ያልማሰው ስር አልነበረም (በነገራችን ላይ ህወሓት ዛሬም ከዐድዋ ድል ጀግኖች ጋር ጥቁር ደም እንደተቃባ በግላጭ የሚያመላክተው በዘንድሮው 118ኛው ክብረ በዓል ላይ የተስተዋለው አሳፋሪ ትእይንት ነው፡፡ ይኸውም በታሪካዊቷ ዐድዋ ከተማ በሚገኘው ሶሎዳ ተራራ ስር ‹ድሉን ለመዘከር› ከተሰቀሉት የእቴጌ ጣይቱ፣ የራስ አሉላ አባነጋ፣ የባልቻ አባነፍሶ እና የባሻ አውዓሎም ግዙፍ ምስሎች መሀል የተሸናፊው ሀገር ህዝብ ሳይቀር በድሉ ዕለት ሮማ በተሰኘው አደባባዩ ‹‹ቪቫ ምኒሊክ›› እያለ በታላቅ ጩኸት ያወደሰው የታላቁ ንጉሠ ነገሥት ምስል አለመካተቱ ነው፡፡ …መቼም ይህ ለምን ሆነ? ብለን የክልሉን አስተዳዳሪ ጓድ አባይ ወልዱን ብንጠይቀው ‹‹በጦርነቱ ወቅት ምኒሊክ መሸሽ ጀምሮ ነበር›› የሚለውን ዝነኛ ህወሓታዊ ትርክት ገልብጦ፣ ‹‹በስራ መደራረብ በተፈጠረ ስህተት ነው›› ብሎ በክፍለ ዘመኑ ታላቅ ሽርደዳ አንጀታችንን ይበልጥ ድብን እንደሚያደርገው ቅንጣት ታህል አትጠራጠሩ)
ለማንኛውም እንደ ፕሮፌሰር እንድሪያስ ያሉ በድሃው ሕዝብ ጥሪት የከፍተኛ ደረጃ የትምህርት ዕድል ማግኘት የቻሉ በርካታ እበላ-ባይ ‹‹ምሁራን›› ስርዓቱ የሥልጣን ዘመኑን ለማራዘም የሚያምታታበትን ‹‹የሁለት ዲጂት የኢኮኖሚ ዕድገት›› የፈረንጅ ጥናቶችን በጥራዝ-ነጠቅነት እያጣቀሱ ምክንያታዊ መስለው ሊያሳምኑን በከንቱ ብዙ ደክመዋል፡፡ በአናቱም የመከላከያ ሠራዊቱ ለባዕድ ሀገር ጥቅም ሲባል ሶማሊያን በወረረበት ወቅት አንዳንድ የዩንቨርስቲ መምህራን እና ‹‹የፖለቲካ ተንታኞች›› በመሬት ያለውን ተጨባጭ እውነታ ይሁነኝ ብለው ወደጎን ገፍተው አገዛዙ ቀን ከሌት ‹‹እመኑኝ!›› በሚል ጩኸት ያሰለቸንን ሰበብ፣ በጥናት እንደተረጋገጠ አስመስለው ለመተንተን ያደርጉት የነበረው እሽቅድምድም ሁሌም በሀዘን የምናስታውሰው ነው፡፡
የኃይማኖት መሪዎችም ምንም እንኳ በነቢብ የአገልግሎታቸው ዋጋ በፈጣሪ መንግስት መሆኑን ደጋግመው ቢነግሩንም፣ በሀልዮ የሚታየው የአሸርጋጅነት ግብራቸው ግን ምድራዊውን ጨቋኝ ስርዓት ደግፎ የሚይዝ ምሰሶና አቅፎ የሚያሞቅ ክንድ ከሆነ በርካታ አስርታት ተቆጥረዋል፡፡ የእስልምና እምነት የበላይ ወሳኝ አካል የሆነው መጅሊስ መእምናኑ ያነሱት ፍትሃዊው የመብት ጥያቄ ተቀልብሶ፣ ሕዝባዊ ውክልና የተሰጣቸው የኮሚቴ አባላት ለአስከፊው የቃሊቲ ማረሚያ ቤት የተዳረጉበትን መንግስታዊ ሽብርተኝነት ለመሸፋፈን ከመተባበርም አልፎ ቅዱስ ቁራንን አዛብቶ እስከመጥቀስ መድረሱ በትዝብት ያሳለፍነው የትላንት ኩነት ነው፡፡ የክርስትና እምነት መሪዎችም በተመሳሳይ ሁናቴ የስርዓቱን የጭካኔ እርምጃዎች እንደ ቅዱስ ተግባር ለማፅደቅ ያልረጩት ጠበል፣ ያልጠቀሱት የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል አልነበረም፡፡ ሌላ ሌላውን እንኳን ትተን በቅርቡ ህይወቱ ያለፈው የኦሮሚያ ክልል አስተዳዳሪ የአለማየሁ አቱምሳ ስርዓተ ቀብር ላይ ፓትርያርክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ‹ዲሞክራሲን ለማስፈን መስዋዕትነት የከፈለ፤ ሩጫውን የጨረሰ፤ ተጋድሎውን
በብቃትና በንቃት የተወጣ…› እያሉ አፋቸውን ሞልተው የምስክርነት ቃላቸውን ሲሰጡ ሀፍረት ብሎ ነገር ለቅፅበት እንኳን ዝር 3 አላለባቸውም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆነ በሰውየው ህልፈት እጃቸው እንዳለበት የሀሜት ወሬ የሚናፈስባቸው እነዚያ ጲላጦሳውያን ጓዶቹ እንዳሻቸው ቢያንቆለጳጵሱት መቼስ የፕሮፓጋንዳ ስራ ነው ብሎ በቸልታ ማለፍ ይቻል ይሆናል፡፡ ነገር ግን የሰማዩን መንግስት ብቻ ያገለግሉ ዘንድ በቃሉ እንዲመላለሱ ግድ የሚላቸው ‹‹መንፈሳውያን››፣ እንዲያ የገዛ ወገኑን ‹‹ኦነግ!›› በሚል የሀሰት ውንጀላ በጥይት ሲደበድብና ሲያስደበድብ፤ መከራን በሕዝብ ላይ እንደምርጊት ሲለስን፤ አምባገነን ስርዓቱን በታማኝነት ሲያገለግል… ያለፈን ሰው ‹‹ዲሞክራት›› እያሉ በአደባባይ ማወደስ በቤተ-ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ ራሱ የተነቀፈውን ለእግዚአብሔርና ለቄሳር ዕኩል መገዛትን እንደትክክለኛ ተግባር አምኖ መቀበል ነው ወደሚል ጠርዝ መገፋታችን አይቀርም፡፡
በግልባጩ በሁሉም እምነት ያሉ ‹‹መንፈሳዊ›› መሪዎች ስርዓቱ በድህረ-ምርጫ 97ም ሆነ በተከታዮቹ ዓመታት የተቃዋሚ ፓርቲ የአመራር አባላትን እና ጋዜጠኞችን እንደ ጥጃ እያሰረ በግፍ ሲያሰቃይ ድርጊቱን ለመንቀፍም ሆነ ዘላቂ ዕርቅ እንዲወርድ ለመማለድ አንዳች ሙከራ አለማድረጋቸው በታሪክ ጥቁር መዝገብ በጉልህ ቀለማት ሰፍሮ የሚኖር ሀጢያታቸው ነው (የቅንጅት እስረኞችን ለማስፈታት የተሄደበት የ‹‹ሽምግልና›› መንገድ የአቶ መለስ ዜናዊ ቧልት ስለመሆኑ ከቶም ማንም ሊጠራጠረው አይችልምና እዚህ መጥቀሱ አስፈላጊ አይመስለኝም)
ሌላው የማሕበረሰባችን የሞራል እሴት በእጅጉ መዝቀጡን የሚያስረግጥልን ብዙሀኑ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች በተዘፈነበት ለመደነስ፣ በተደገሰበት አሳላፊ ለመሆን የሚያደርጉትን መገፋፋት ስናስተውል ነው፡፡ ስርዓቱ ከሚያራምደው ‹‹አብዮታዊ ዲሞክራሲ›› ርዕዮተ-አለም የተቀመረውን ‹‹ፌደራሊዝም አወቃቀር››ን ተንተርሶ ሀገሪቱን በዘውግ ከፋፍሎ እና በሕዝብ መካከል የጥርጣሬ መንፈስ አንብሮ የሥልጣን ዕድሜ ማራዘሙን በግጥምና ዜማ ማወደስ የእህል-ውሃ ጥያቄ ካደረጉት በርካታ ዓመታት ነጉደዋል፡፡ እንዲህ አይነት የሙዚቃ ስራ በአንዳንድ ክልሎች መሬት የሚያሸልም ፈጣን አዋጪ አድርባይትመንት (ኢንቨስትመንት ላለማለት ነው) እስከ መሆን መድረሱ ከታፊና ነጋዴ አርቲስቶች በዘውጉ ዙሪያ ይረባረቡ ዘንድ ታላቅ ልማታዊ አብነት ሆኗቸዋል፡፡ ይህ ሁናቴም በኢትዮጵያ ኪነ-ጥበብን የንፁሃን መታጣት ከድንጋይ ወገራ የታደጋትን የኦሪቷ ዘማዊት ከማስመሰልም አልፎ እንደ ነገሥታቱ ዘመን የአዝማሪ ጨዋታ፤ የቤተ-መንግስቱ መዝናኛ እና አጀንዳ ማራገቢያነት እስከ መሆን ሞዴል ተሸላሚ አድርጓታል፡፡ ይሁንና ቁጥራቸው ጥቂት ቢሆንም ቴዎድሮስ
ካሳሁንን (ቴዲ አፍሮን) የመሳሰሉ መክሊታቸውን እንደ ጉሊት ሽንኩርት ለሽያጭ ያላቀረቡ ከያኒያን፣ ደራሲያን፣ ገጣሚያን… የመኖራቸውን እውነታ ሳንዘነጋ፤ ሀገሪቱ ‹‹ሰው አይብቀልብሽ!›› ተብላ የተረገመች እስኪመስል ድረስ ብሔራዊ ጥቅም፣ ህሊና፣ ሞራል፣ እውነት የረከሱበትና የተዋረዱበት ዘመን ላይ መድረሷን የሚያስረግጡልን በርካታ ማሳያዎች አሉ፡፡
ከጥቂት ወራት በፊት በብአዴኑ ካሳ ተክለብርሃን ፊት-አውራሪነት የሶማሌ ክልልን የጎበኙት አርቲስቶቻችን፣ ገና ድሮ ጆርጅ ኦርዌል ‹‹Animal Farm›› ብሎ በሰየመው መጽሐፉ ‹‹አራት እግር ጥሩ፤ ሁለት እግር መጥፎ›› እያሉ በመንጫጫት ስብሰባን ለመረበሽና ተቃውሞን ለማጨናገፍ አሳማው ናፖሊዮን እንዳሰለጠናቸው አይነት በጎች፤ ኢህአዴግ በጎጥ የካፋፈለውን ሕዝብ ‹‹በታሪኩ ከመቼውም ጊዜ በላይ አሁን አንድ ሆኗል!!›› በማለት በሬ ወለደ የሀሰት ምስክርነታቸውን አምነን እንድንቀበል ለማድረግ ለሳምንታት ተንጫጭተው ሊያደነቁሩን ሞክረዋል፡፡ እነዚህ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች የክልሉ ነዋሪዎች ገና ዛሬ (በኢህአዴግ እፁብ ድንቅ እና ፍትሀዊ አስተዳደር) ኢትዮጵያዊነት እንደተሰማቸው፤ ገና ዛሬ በፍቃደኝነት ኢትዮጵያውያን እንደሆኑ አስመስለው ለማሳመን የሄዱበት የቁልቁለት መንገድ አጥንት ድረስ በሚዘልቅ ሀዘን እንዳኮራመተን እነርሱም ይጠፋቸዋል ብዬ አላስብም፡፡ ጉዳዩ ሆድ ሌላ፣ እውነት ሌላ ሆኖባቸው እንጂ፡፡ ግና፣ የቄሳሩ ጲላጦስም ‹‹እውነት ምንድር ነች?›› እንዲል፣ እውነት ለእነርሱ ዋጋዋ ስንት ነው? መቼም ከእውነት ይልቅ ግድ የሚሰጣቸው የሆድ ነገር ነው፤ እበላ አዳሪዎች ናቸውና፡፡
በጥቅሉ በኢትዮጵያችን ከምሁር እስከ ተርታው፤ ከጳጳሳት (ፓስተራት) እና ሼሆች እስከ መናፍቃውያን፤ ከልሂቅ እስከ ደቂቅ፤ ከጄነራል እስከ ወታደር፤ ከከያኒ እስከ ጽሑፍ ገልባጭ፤ ከቱጃር እስከ ጥሮ-ግሮ አዳሪ፤ ከመምህር እስከ ተማሪ… ስር የሰደደ አድርባይነት እና የሞራል ክስረት ለመንሰራፋቱ አይነተኛ ማሳያው አምባገነኑ ኢህአዴግ እንዲህ ሚሊዮኖችን ረግጦ እየጨፈለቀ፣ አስሮ እያንገላታ፣ ከሀገር እያሰደደና እየገደለ… ከሁለት አስርት በላይ መቆየት የመቻሉ ምስጢር ነው፡፡ ግና፣ የሕዝብን መከራ በማራዘም ኪስን ማደለብ፣ ግላዊ ፍላጎትን ማርካት ሁሌም አትራፊ ሊሆን እንደማይቻል መዘንጋት የለበትም፡፡ ማን ነበር ‹የተከፋፋለና አድርባይ ሕዝብን ከጭቆና ማላቀቅ፣ ሰማይን የማረስ ያህል አዳጋች ነው!› ያለው?
አዎን፣ ከ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ጀምሮ በጉልበታም ስርዓታት የጭካኔ መዳፍም ሆነ በግላዊ ጥቅመኝነት እየተናዱ የመጡት የባህል እና የሞራል እሴቶች ትውልዱን ዛሬ ላይ ለደረሰበት አስከፊ ማሕበራዊ ቀውስ መዳረጋቸው አሌ የማይባል ነው፡፡ ርግጥ ነው የችግሩ ስፋትና ጥልቀት እንደ ስርዓቱ የፖለቲካ ፍልስፍና በዘውግ የተከፋፈለ አይደለም፤ ብዙሀን እና ህዳጣን የሚል መስፈርትንም የተከተለ አይደለም፤ ኃይማኖታዊ መለያም የለውም፤ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች አለቅጥ መንሰራፋቱ በግላጭ ይታያልና፡፡ ይህም ነው መፍትሔውን ስር ነቀል የማሕበራዊ አብዮት (ለውጥ) ብቻ እንዲሆን ያስገድደው፡፡
የቀደሙት ሁለት አብዮቶች በዋናነት ያነሷቸው የብሔር እና የመሬት ጥያቄ መክሸፋቸው (መቀልበሳቸው) ዛሬም ሶስተኛ አብዮትን የማይቀር ዕዳ አድርጎ የመውሰዱ ሁነት እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ሥራ-አጥነት፣ ከነባሩ ባህል ማፈንገጥ፣ ሙስና፣ በሕብረተሰቡ ዘንድ አክብሮትና 4 ተሰሚነት ያላቸው ታላላቆችን አለማደመጥ፣ አድርባይነት፣ ደንታቢስነት፣ ዶሮ ሳይጮኽ ደጋግሞ መክዳት፣ የ‹‹ስቀሎ፣ ስቀሎ…›› ሀሰተኛ ድምፅ መበራከት፣ ኢ-ሞራላዊ ድርጊቶች እና የመሳሳሉት ትውልድና ሀገር ገዳይ ደዌዎችን ለመፈወስ ከማሕበራዊ አብዮት ያነሰ መፍትሔ እንደሌለ ከተለያዩ ሀገራት ታሪክ መረዳት ይቻላል፡፡ በነገራችን ላይ ኢህአዴግ በየትኛውም የዓለማችን ሀገራት የተከሰተ ሕዝባዊ አብዮት እንቅልፍ እንደሚነሳው በርካታ ማሳያዎች አሉ፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ለተከታታይ ቀናት ‹‹ተንታኝ›› ጭምር በመጋበዝ፣ ምስራቅ አውሮፓ ድረስ ተጉዞ የተሳካውን የዩክሬን አብዮት ከቀለም ጋር በማያያዝ ለማውገዝ ያቀረባቸው ፕሮግራሞች የፍርሃቱ መጠን አንዱ ማሳያ ተደርገው ሊወሰዱ ይችላል፡፡ ግና፣ እውነት እውነት እልሀለሁ በመቶ ሺህ የሚቆጠር የታጠቀ ኃይል ቢሰለፍ፣ እልፍ አእላፍ ፊርማቶሪዎች በሕዝብ መሀል ቢሰገሰጉ፣ ሚሊዮናት ካድሬዎች ሀገር-ምድሩን ቢያጥለቀልቁ፤ አገዛዛዊ ጭቆና እና ማሕበራዊ ክስረት እስካለ ድረስ የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ፣ የትኛውም ምድራዊ ኃይል ሊያመክነው የማይችል አብዮት መቀጣጠሉ የማይቀር ጉዳይ ነው፡፡ በመጨረሻም ይህንን ጽሑፍ ጄነራል መንግስቱ ነዋይ በተለምዶ ‹‹የታሕሳስ ግርግር›› እየተባለ የሚጠራውን የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መክሸፍ ተከትሎ ፍርድ ቤት በቀረበበት ወቅት በሰጠው ቃል እቋጨዋለሁ፡-
‹‹…ዋ! ዋ! ዋ! ለእናንተም ለግዥአችሁ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሀሳቤ በዝርዝር ገብቶት በአንድነት በሚነሳበት ጊዜ የሚደርስባችሁ መዓት የሚያሳቅቅ ይሆናል፡፡››
ትንቢቱ ከ13 ዓመት በኋላ ከእጥፍ በላይ መፈፀሙን ስናስታውስ፣ በጥቅመኝነት ስሌት ከስርዓቱ ጋር ተወዳጅተው የግፉአንን የመከራ ዕድሜ የሚያራዝሙ አድርባዮችም ሆኑ የአገዛዙ ልሂቃን ሕዝቡ ‹‹ሆ!›› ብሎ በአንድነት የተነሳ ዕለት ከመዓቱ ያመልጡ ዘንድ አይቻላቸውምና ዛሬውኑ ‹ንሰሀ ግቡ!› ብሎ ማሳሰብ ግድ ይላል፡፡ …ዋ! ዋ!! ዋ!!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live