Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

በኩዌት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ አሳሳቢ ሆኗል

0
0

ምኒልክ ሳልሳዊ

በዚህ ሳምንት አትክሮት ማግኘት ከሚፈልጉ ወገኖቻችን በዋነኝነት በኩዌት የሚኖሩ እና በስራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ናቸው:: ባሳለፍነው ቀናት በዋና ዜናነት በአገሪቱ የስፖርት ሚኒስትር መኖሪያ ቤት ውስጥ የምትሰራ ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ የአሰሪዋን ሴት ልጅ ገላለች ተብሎ የተዘገበውን ዜና ተከትሎ ኢትዮጵያውያን በስጋት ላይ ሲሆኑ እንዲሁም ተከራካሪ የዜግነት መብታቸውን የሚያስከብር ኤምባሲ መጥፋቱ እና በኤምባሲው የሚፈጸመውን ደባ በከፊል ለማየት እንሞክራለን::

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)

በአሁኑ ወቅት በኩዌት ለኢትዮጵያውያን ነገሮች ሁሉ አስቀያሚ እና አስቸጋሪ እየሆኑ እንደሆን ለኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ቅርብ የሆነ ኢትዮጵያዊ ገልጿል::ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደረጉ በደሎች ተከራካሪ የመንግስት አካል እና የኤምባሲ ሰው መጥፋቱ ለአሁኑ ወንጀል መፈጸም እና ስጋት መንስኤ እንደሆነ ጠቁሟል::በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሱ በደሎች እና ከአሰሪዎቻቸው እና ከቀጣሪ ድርጅቶች ጠፍተው የሚመጡ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሃገራቸው መመለስ ሲገባው ከደላሎች ጋር በመመሳጠር ሌላ ስራ በማስገባት ችግሩ እንዲሰፋ ያደረገው እምባሲው እና ሆዳም ዲፕሎማቶቹ ናቸው ሲል ይኸው የኮሚኒቲው ሰው ገልጿል::

ኢትዮጵያውያን በኩዌት እስር ቤት እየተሰቃዩ ከፍተኛ ወጪ ከኤምባሲው እና ከኮሚኒቲው በማውጣት ደግሰው በመጨፈር ላይ በነበሩበት ሰአት ከዚህ ቀደም ከፍተኛ ተቃውሞ የገጠማቸው ሲሆን ወገኖቻችን በእስር ቤት እየተሰቃዩ ለምን እንዲህ አይነት ድግስ ይደገሳል:: አስፈላጊውን ወጪ በማድረግ ወደ ሃገራቸው የሚመለሱ ይመለሱ ያሉ ወገኖችን የተለያየ የኤምባሲ ትብብር በመከልከል ወደኤምባሲው በር እንዳይደርሱ በማገድ ከፍተኛ የሆነ የግል ጥቅምን ያማከለ በደል እየተፈጸመ መሆኑን የኮሚኒቲው ሰው አጫውቶናል::ለማንም ተደግሶ የማያውቅ ኮሚኒቲው የኢትዮጵያ ሆኖ እያለ ለሌሎች ኢትዮጵያውያን እና ግለሰቦች ሳያገለግል የትግራይ ልማት ማህበር አላማን ሲያስተምር ይውላል ሲሉ አባላቱ ይተቹታል:: የታሰሩትን ለጊዜው ተወት አድርጓቸው እና የሃገራችንን መልካም ገጽታ እናስተዋውቅ እያሉ ለዜጎች አትኩሮት በመንፈግ አሁን ላለንበት ስጋት አብቅተውናል ሲሉ ኢትዮጵያውያን በማማረር ይናገራሉ::

ኮሚኒቲው ሲቋቋም ለታሰሩ እና ለተቸገሩ መፍትሄ ይሆናል ተብሎ የነበረ ቢሆንም በስሙ መካከል ህዳሴ የሚል ቃል በመጨመር ቢሮውን ከነበረበት ቦታ ወደ ኤምባሲው ውስጥ በማዘዋወር ፖለቲካ እየሰበከ ኢትዮጵያውያንን ረስቷል ሲሉ ይናገራሉ::ሌላው ነገር ይላሉ ኢትዮጵያውያኑ ማንኛውንም ደብዳቤ በኤምባሲውም ይሁን በኮሚኒቲው ማህተም ተደግፎ ቢጻፍ በኩዌት ውስጥ ተቀባይነት የለውም ሲሉ ይገልጻሉ::የመኖሪያ ፈቃድ ለማሳደስ በእጃችን ፓስፖርት እያለ ፓስፖርቱን ለመቀበል የኩዌት መኖሪያ ፈቃድ የሚያድሰው አካል ብዙ መጉላላት እና ወከባ እንደሚፈጽምባቸው እና ይህንንም ለኤምባሲው ሪፖርት ቢደረግ የራሳችሁ ጉዳይ የሚል ዘለፋ አዘል መልስ እንደሚሰጡ ታውቋል::

በግድያ ወንጀል ተጠርጥራ የተያዘችው ኢትዮጵያዊት ተከትሎ የመኖሪያ መታወቂያዎች እንዲታደሱ መደረግ የጀመረ ሲሆን ካሁን በፊት NON KUWAITI የሚል ሲጻፍ የነበረ ሲሆን በኣሁን ሰአት ለኢትዮጵያውያን በተለየ መልኩ Ethiopian ኢትዮጵያዊ የሚል መጻፍ የተጀመረ መሆኑ ታውቋል::
የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ምንም መከራከር የማይችል እና በመኪና ተገጭተው የሞቱ ታንቀው ራሳቸውን ከፎቅ ወርውረው የሞቱ ኢትዮጵያውያን ደብዛቸው እና የሞት ጉዳያቸው እንዳይነሳ ኮሚኒቴው በመሸፋፈን ለችግር እየዳረገን ነው ሲሉ በኮሚኒው ላይ አማረዋል::በ17 አመቷ ወደ ኩዌት የገባችው እና በአሁን ሰአት የ22 አመት ወጣት የሆነችው በግድያ ተጠርጥራ የተያዘችው ኢትዮጵያዊት በአሰሪዎቿ ልጆች የተደፈረች መሆኗን ለኤምባሲው ቅርብ የሆነ ግለሰብ ተናግሯል::ግድያውን ከመፈጸሟ በፊት በልጁ የተደፈረች እና ይህንን ጉዳይ ለሴት ልጂቷ ብትናገር የሚሰማት ያጣት እና የደበደቧት መሆኗን እና ይህንን ተከትሎ ወንጀሉን ፈጽማው ይሆናል የሚሉ ግምቶች በስፋት ይነገራል::

በኢምባሲው ውስጥ የሚደረገው ከፍተኛ በደል በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ሲሆን በኤምባሲው ውስጥ ከ400 እስከ 500 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን የሚገኙ ሲሆን: ከፍተኛ የሆነ መጉላላት እየደረሰባቸው ለኣእምሮ ጉዳት ለጭንቀት ለድብርት እና ለእብደት መዳረጋቸውን የገለጹ ሲሆን በኤምባሲው ውስጥ ከፍተኛ የምግብ እጥረት ያለ ሲሆን ኤምባሲው ግን በድግስ እየተንበሸበሸ ኮሚኒቲው በየድህረገጹ የፌሽታ ፎቶዎችን በመርጨት ከፌሽታው ጀርባ ግን የኢትዮጵያውያን ሞት እና ሰቆቃ ለእይታ እንዳይበቃ እያደረገ ሲሆን አንድም ቀን የሞቱ እና የተበደሉ ኢትዮጵያንን ቦታ ሳይሰጥ የኢትዮጵያውያን መብት እና ነጻነት ሳያስከብሩ በአደባባይ ስንገላታ እያዩን ያላግጡብናል ያመናጭቁናል ከፖሊስ ጋር ይተባበሩብናል በማለት አቤቱታቸውን የሚሰማ አካል እንዳላገኙ እና በስጋት አጣብቂኝ ውስጥ መግባታቸውን ኢትዮጵያውያን ተናግረዋል:: ተጨማሪ ዘገባዎች ካሉ እንመለሳለን::


ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ስነምግባር ደንብ እንደማይፈርም አስታወቀ

0
0

በ2002ቱ ጠቅላላ ምርጫ መቃረቢያ ላይ ከ60 ያላነሱ ሀገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፓርቲዎችም እንገዛበታለን ብለው ከፈረሙበት በኋላም ሕግ ሆኖ የወጣው የስነ-ምግባር ደንብ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ እንደማይፈርም አስታወቀ። የፓርቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ለሰንደቅ እንደተናገሩት፤ የምርጫ ስነ-ምግባር ደንብ በሀገሪቱ ፓርላማ ሕግ ሆኖ እስከወጣ ድረስ ፓርቲው እንደገና የሚፈርምበት ምክንያት የለም ብለዋል።
Yilkal Getnet
ኢህአዴግን ጨምሮ ዘጠኝ ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች በሚሳተፉበት የፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለመግባት እንደ ቅድመ ሁኔታ እየቀረበ ያለው የምርጫ የስነ-ምግባር ደንብ በቅድሚያ ፈረሙ የሚባለውን “እኛ እንደቁምነገር አንቆጥረውም” ሲሉ የመለሱት ኢንጂነሩ ከኢህአዴግም ጋር የሚደረግ ማናቸውም ውይይት በቅድመ ሁኔታ ላይ መመስረት እንደሌለበት ገልፀዋል። በቅድመ ሁኔታ ላይ የተመሠረተ ውይይትም ሆነ የጋራ ምክር ቤት የምክር ቤቱን ነፃነት ጥያቄ ላይ የሚጥል ስለሆነ ለመነጋገርና ለመወያየት የምርጫ ስነ-ምግባር ደንብ ፊርማ እንደቅድመ ሁኔታ መቅረብ የለበትም ብለዋል።
“አሁን ተቋቁሟል የሚባለው የፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት በራሱ ብዙ ችግር ያለበት፣ ኢህአዴግና ደጋፊዎቹ ተሰብስበው የሚቀልዱበት እንጂ ሐቀኛ ሆኖ በነፃነት ውይይት የሚደረግበት ም/ቤት አይደለም” ሲሉ ኢንጂነር ይልቃል ተናግረዋል። ስለሆነም ፓርቲያቸው ለጊዜው በፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት የመሳተፍ ፍላጎት የለውም ብለዋል።

ከኢህአዴግ ጋር ለመነጋገርም ሆነ ተቀራርቦ ለመወያየት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መሆን እንዳለበት የጠቀሱት ኢንጂነሩ ሕጋዊ ፓርቲዎች ሆነን በምርጫውም እንደምንሳተፍ ሰለሚታወቅ ሌላ የተለየ ቅድመ ሁኔታ አያስፈልግም፣ ወደፊርማ የሚያስገባ ሕጋዊ መሠረት የለም ብለዋል።
ኢንጂነር ይልቃል ወደፊርማ የሚያስገባ ሕጋዊ መሠረት የለም ቢሉም፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ስነ-ምግባር ለመደንገግ በወጣው አዋጅ 662/2002 ዓ.ም አንቀጽ 21(6) እና (7) ላይ አዋጁ እንዲወጣ ተስማምተው በፈረሙ ፓርቲዎች እንደሚቋቋምና የስነ ምግባር ደንቡ ሲቀርፅ በልዩ ልዩ ምክንያት ያልተሳተፉ ሌሎች ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤቱ የሚያወጣውን የስምምነት ሰነድ መፈረም እንዳለባቸው ያስገድዳል።

ይሁን እንጂ፤ “የምንፈርመው ነገር የለም” ያሉት ኢንጂነር ይልቃል ፓርቲያቸው በዚህ ውስጥ የመሳተፍ ፍላጎት እንደሌለው አረጋግጠዋል። በምርጫውም የሚኖራቸው ተሳትፎም ደንቡን በመፈረምና አለመፈረም ላይ የተመሠረተ ሳይሆን በአጠቃላይ ገዢው ፓርቲ የፖለቲካውን መድረክ ጨምድዶ በያዘበት ሁኔታ ነው ብለዋል። አሁን ባለው ሁኔታም ምርጫው ፍትሐዊ ይሆናል ብለው እንደማያስቡ ነገር ግን መብቱን የማስከበር የሕዝቡ እንጂ የኢህአዴግ መልካም ፈቃድ አይደለም ሲሉ አስረድተዋል።
blue party
በቅርቡ ኢህአዴግ በመወከል ወደ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት አባልነት የተዛወሩት የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ደስታ አስፋው በበኩላቸው ማንኛውም ፓርቲ የፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ለመግባት በማመልከቻ መጠየቅ እንዳለበት ሀገር አቀፍ ፓርቲ መሆንና በጥር ወር 2002 ዓ.ም የወጣውን የፖለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ ስነ-ምግባር ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 662/2002 ዓ.ም መፈረም አለበት ብለዋል። ፓርቲዎቹ ወደ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ሲመጡ የስነ-ምግባር ደንቡን እንዲፈርሙ የሚያስገድደው በፓርቲዎች ስምምነት ሕግ ሆኖ የወጣው አዋጅ እንጂ ኢህአዴግ አለመሆኑንም አያይዘው ጠቅሰዋል።

ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ

ቀዳማይ ወያኔ፤ ዓድዋ እና የካቲት 11 በወያኔ ትግሬዎች ዕይታ –ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያ ሰማይ አዘጋጅ)

0
0

ከላይ በግራ በኩል የሚታየው ፎቶግራፍ፤ የቀዳማይ ወያኔ መሪ ብላታ ሃይለማርያም ረዳ ለዳግማይ ወያነ መሪ ለመለስ ዜናዊ በቀዳማይ ወያኔ የተገለገሉበት የጦር ሜዳ መነፅር ሲያስረክቡት ነው።

ከላይ በግራ በኩል የሚታየው ፎቶግራፍ፤ የቀዳማይ ወያኔ መሪ ብላታ ሃይለማርያም ረዳ ለዳግማይ ወያነ መሪ ለመለስ ዜናዊ በቀዳማይ ወያኔ የተገለገሉበት የጦር ሜዳ መነፅር ሲያስረክቡት ነው።


ብዙዎቹ በዚህ ጽሑፍ የቀረቡ መረጃዎች እና ትንታኔዎች በሂደት ላይ ካለ ከሚቀጥለው አዲስ መጽሐፌ የተገኙ ምንጮች ናቸው።እኛ በታሪክ አጋጣሚ ተገኝተን ጸረ ወያኔ አቋም ይዘን የምንተነትን ጸሐፊዎች የተቻለንንን ያህል የወያኔ ቅጥፈቶች እያጠናን ስናቀርብ ማንበብ ሰልችቶአቸው ግማሽ ገጽ አንብበው ወደ ቀላል ዜና እና ትንታኔ የሚሮጡ ብዙ እንደሆኑ አገምታለሁ።እንዲህ ዓይነት ልምድ ጥልቅ እውቀት እንዳይኖረን ያግደናል።እንድያ ከሆነ የሚሞግቱንን ጠላቶች በማስረጃ ለመመከት ደካሞች እንሆናለን።መረጃ ሲያጥረን ሕዝቡ የጠላት ‘ፕሮፓጋንዳ’ ተማሪ ይሆናል።። ስለዚህም ብርቱ ድካም፤ምርምር ጌዜ እና መስዋእት የተደረገባቸው ጽሑፎች ማንበብ ድርሻችሁ እንደሆነም አትዘንጉ።

ባለፈው በክፍል ፩ “የወያኔ ትግሬዎች በጉንደት፤በጉራዕ፤በዶጋሊ ፤….ጦርነቶች የሚዋሹት ውሽት ሲመረመር” በሚል ለብዙ አመታት ሲነግሩን የነበረውን “የወቅቱ ጦርነቶች” የገጠሙት ትግሬዎች ብቻ ነበሩ፤ እያሉ የሌሎች ኢትዮጵያዊያን ተሳትፎ ዋጋ በማሳጣት ሲዋሹን የነበረው ጀብደኛ ትምክሕት በጐንደር፤በጐጃም፤በወሎ እና በሸዋ ጦር ተዋጊዎች ጭምር እየታገዙ ጦርነቱን ገጥመው ድል የተቀዳጁ አንደነበር አንጂ ትግሬ ብቻውን እንዳልተዋጋ እና ድሉም የብቻችን ነው የሚለው የወያኔ የታሪክ ቅሚያ እንደበፊቱ በቸልተኛነት መታለፍ እንደሌለበት ከሃቅ የራቀ ውሸታቸውን በወቅቱ የተጻፉ መረጃዎች በማስረጃ አጋልጫለሁ። ክፍል ፪ “የዓፋሮች እና አፄ ዮሐንስ ፍትግያ” የሚለው ጽፌ አዘጋጅቼው ልለጥፈው ነበር፤ እሱን ወደ ክፍል ሦስት በማቆየት ይህ ክፍል ሁለት ብለን በመሰየም እናንብበው።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

በጋዜጠኞች ላይ ያለ ማስረጃ የሚሰነዘሩ ውንጀላዎች ባስቸኳይ እንዲቆሙ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ጠየቀ

0
0

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ)= ETHIOPIAN JOURNALISTS FORUM (EJF)

ጋዜጣዊ መግለጫ፦

ማህበራችን ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዶ የምዝገባ ሰርተፊኬት ለማግኘት የጀመረው እንቅስቀሴ በቅርቡ ከመንግስት አወንታዊ ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ በማድረግ የተቋቋመለትን አላማ ለማሳካት እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን መብትና ጥቅም ከማስጠበቅና የመናገር ነፃነትን ከማበረታታት ባለፈም ከአህጉራችን አፍሪቃ ጋዜጠኞች ጋር በመተባበር የመላው አፍሪቃ ጋዜጠኞችን መብትና ጥቅም የሚያስጠብቅና የመናገር ነፃነትን የሚያበረታታ አህጉራዊ ተቋም ለመመስረት ተነሳሽነትን ወስዶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ በቅርቡም የምስራቅ አፍሪቃ ጋዜጠኞችን በማስተባበር አህጉር አቀፍ እንቅስቃሴያችንን ለማስጀመር ዝግጅት እያደረግን ነው፡፡
newspaper_for_rent
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተግባር ጋዜጠኛውን ሳይወክሉ የጋዜጠኛውን ስም የያዙት የኢጋማ፣ የኢነጋማና የኢብጋህ አመራሮች ነን የሚሉት ግለሰቦች በመቀናጀት በየሚዲያው እየቀረቡ ጋዜጠኞችንና የሚዲያ ተቋማትን ለማሸማቀቅ ያለመ ውንጀላና አሉባልታ የመንዛት ዘመቻ ጀምረዋል፡፡ ግለሰቦቹ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ቀርበው በጋዜጠኞች ላይ ከሽብር ፈጠራ እስከ ሀገር ማተራመስ የደረሰ የውንጀላ መዓት ቢደረድሩም አንዳችም ማስረጃ አላቀረቡም፡፡

ለምሳሌ የካቲት 22 ቀን 2006 ዓ.ም በታተመው አዲስ አድማስ ጋዜጣ (ቅጽ13 ቁጥር 737) ላይ ስማቸውን ደብቀው ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ጋዜጠኞች ሀገር ለማተራመስና ሽብር ለመፍጠር እየተዘጋጁ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ይሁን እንጂ “ምን ማስረጃ አላችሁ” ለሚለው የጋዜጠኛዋ ጥያቄ የመለሱት “እኛ እና እነሱ እንተዋወቃለን፡፡” የሚል አስገራሚ መልስ ነው፡፡ ይህ መሰረተ ቢስ ውንጀላ ጋዜጠኞችን ለማሸማቀቅ የተወረወረ በመሆኑ የኢጋማ፣የኢነጋማና የኢብጋህ አመራሮች ነን የሚሉት ግለሰቦች ጋዜጠኞችን እና የሚዲያ ተቋማትን ያለ ማስረጃ መወንጀላዎች ባስቸኳይ እንዲያቆሙ ይጠይቃል፡፡

ejf
በመቀጠልም በሪፖርተር ጋዜጣ (የዕሁድ እትም ቅፅ 19 ቁጥር 1446) የካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም “ኢጋማ በምስረታ ላይ ያለውን የጋዜጠኞች መድረክ አስጠነቀቀ” የሚል ዜና ተመልክተናል፡፡ ሆኖም በጋዜጠኞች ስም ተሰባስበው ጋዜጠኛውን የሚጠቅም አንዳች እንቅስቃሴ ሳያደርጉ ከመተኛታቸው ብዛት አልጋቸው ለረገበ ማህበራት ማስጠንቀቂያ ምላሽ በመስጠት ጊዜ በመሆኑም ምለሻችን በዝምታ መስራት ነው፡፡ የግለሰቦቹ የውንጀላ ንግግር የሚያስረዳው ከህግ፣ ከሞራል እና ከሙያዊ ስነምግባርም በላይ ራሳቸውን ለመሾም የሚፍጨረጨሩ መሆኑን ነው፡፡ ግለሰቦቹ በተለያዩ ጊዜያት መንግስት የፕሬስ ተቋማት ላይና ጋዜጠኞች ላይ የወሰዳቸውን ኢ-ህገመንግስታዊ እርምጃዎች እንደ ጋዜጠኛ ማህበር መሪ ከመኮነን ይልቅ የመንግስትን እርምጃ ሲያወድሱ ተስተውለዋል፡፡ በተጨማሪም በእስር ላይ ሆነው ህክምና በመከልከላቸው ለከፋ ስቃይ ስለተዳረጉ ጋዜጠኞችም ትንፍሽ ሲሉ አልታየም፡፡ እነዚህ የጋዜጠኛ ማህበራት መሪዎች ነን ያሉት ግለሰቦች እንደማህበር መሪ ሳይሆን እንደ ስለላ ተቋም ጋዜጠኞች እና አንዳንድ የሚዲያ ተቋማት ሃገር ለማተራመስና የሽብር ጥቃት ለመፈፀም እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ መረጃ እንዳላቸው በይፋ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም

1ኛ. የሶስቱ ማህበራት መሪዎች አለን የሚሉትን መረጃ ለመንግስት በአፋጣኝ ሳይሰጡ መቆየታቸው በሀገራችን ህግ መሰረት ሊጠየቁው እንደሚገባ እንዲሁም
2ኛ. የሶስቱ ማህበራት መሪዎች በጋዜጠኞች እየተቀነባበረ ነው ካሉት የሽብርና ሀገር የማተራመስ እንቅስቃሴ ጀርባ እንዳሉ የጠቀሷቸውን ኤምባሲዎች በግልፅ ጠቅሰው ለመንግስት እና ለህዝብ እንዲያስታውቁ እንጠይቃለን፡፡

** ** **
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ)
መጋቢት 10 ቀን 2006 ዓ.ም

“ከዚህ በኋላ ትዕግስታችን ተሟጧል!” –ሰማያዊ ፓርቲ በኢትዮጵያ እንደገና ወኔ የተሞላበት የትግል መንፈሱን በማደስ ጥንካሬውን አሳየ!

0
0

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

እ.ኤ.አ ማርች 9/2014 የተከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች በዓል ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ ተዘጋጀቶ በነበረው የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶችም ተሳትፎ አድርገው ነበር፡፡ ከዴሞክራሲያዊ ምርጫ ባፈነገጠ መልኩ በኃይል በስልጣን ኮርቻ ላይ ተፈናጥጠው ስልጣንን የሙጥኝ በማለት ከህግ አግባብ ውጭ በህዝብ ላይ ደባ በመፈጸም ላይ የሚገኙትን የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች ዕኩይ ምግባር የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲገነዘበው በማሰብ ወጣት ሴቶቹ እውነታውን ያለምንም መሸፋፈን በማጋለጥ እምቢ አሻፈረኝ በማለት ተቃውሟቸውን ለዓለም በይፋ አሰምተዋል፡፡ እንዲህ በማለትም ተቃውሟቸውን አጠናክረዋል፣
New Picture (17)
“ከዚህ በኋላ ትዕግስታችን ተሟጧል! ተርበናል! ነጻነት እንፈልጋለን! ነጻነት እንፈልጋለነ! እስክንድር ይፈታ! አንዷለም ይፈታ! አቡባከር ይፈታ! ርዕዮት ትፈታ! የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ ይፈቱ! ፍትህ እንፈልጋለን! ነጻነት! ነጻነት! ነጻነት! አትከፋፍሉን! ኢትዮጵያ አንድ ነች! አንድ ኢትዮጵያ! ከዚህ በኋላ ትዕግስታችን ተሟጧል! ውኃ ናፈቀን! መብራት ናፈቀን! ተርበናል!…“

ለሰማያዊ ፓርቲ ሴት ወጣት አመራሮች ባርኔጣዬን ዝቅ በማድረግ ከወገቤ ጎንበስ በማለት ያለኝን አድናቆት ልገልጽላቸው እፈልጋለሁ፡፡ በእነርሱ እጅጉን ኮርቻለሁ፡፡ ባለፉት ጥቂት ወራት ሰማያዊ ፓርቲን ለምን እንደደገፍኩ እና በጽናትም ከፓርቲው ጎን ለምን እንደምቆምኩ በርካታ ሰዎች ጥያቄዎችን አቅርበውልኝ ነበር፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ቁጥር አንድ አድናቂ (አንደኛ ቲፎዞ) ለምን እንደሆንኩ ማንም ቢሆን ጥያቄዎች ካሉት/ካሏት ይህንን ቪዲዮ (እዚህ ይጫኑ) እንዲመለከቱት እጋብዛለሁ፣ እናም መልሱን ከእዚያው ያገኙታል፡፡

አረመኔው ገዥ አካል በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያን ወጣት ሴቶች እና ወንዶች በዱላ እየደበደበ እና እንደ እባብ እየቀጠቀጠ ሁሉንም የጭቆና ዓይነቶች በእነርሱ ላይ እየተገበረ ባለበት ሁኔታ ከዳር ቆሜ ለመመልከት ህሊናዬ ሊፈቅድልኝ አይችልም፡፡ የመናገር መብታቸውን ተጠቅመው ሀሳባቸውን ለመግለጽ በመሞካራቸው ምክንያት ብቻ የኢትዮጵያ ወጣቶች ሲታሰሩ፣ ሲደበደቡ፣ ሲሰቃዩ እና ግፍ ሲፈጸምባቸው በዝምታ አልመለከትም፡፡ በወጣቶቹ ላይ የሚፈጸመውን ግፍ እና ስቅይት የእነርሱ ድምጽ በመሆን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እናገራለሁ፡፡

ወጣት ሴቶቹ ተቃውሟቸውን የገለጹት በሰላማዊ መንገድ ነው፡፡ በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን በማሰማታቸውም በጨካኙ የገዥ አካል ማሰቃየት ተፈጽሞባቸዋል፡፡ በሰላማዊ እና ከአመጽ በጸዳ መልኩ በአገሪቱ ውስጥ ለውጥ ለማምጣት ሲሉ ነው በአሁኑ ጊዜ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በመሰቃየት ላይ የሚገኙት፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ሴት ወጣት አመራሮች እና አባላት እንደማንኛውም ሰው ሁሉ የ5 ኪ/ሜ ሩጫውን ተቀላቀሉ፡፡ በሰላማዊ መንገድ እሮጡ እና ከማጠናቀቂያ ቦታው ደረሱ፡፡ ምንም ዓይነት ህግ አልጣሱም፡፡ አንድም ጠጠር አልወረወሩም፡፡ በማንም ላይ ጥቃት አልፈጸሙም፡፡ ምንም ዓይነት ሁከትን በሚያመጡ ተግባራት ላይ አልተሳተፉም፡፡ ከአንድ ሺህ በላይ ሯጮች በተሳተፉበት በዚያ ሩጫ ላይ የሰማያዊ ፓርቲ ሴት ወጣት አመራሮች እና አባላት በመሳተፋቸው (ወይም በሌላ ምክንያት) በአንድም ሰው ላይ ጉዳት አልደረሰም፡፡ ቅንጣት ያህል ንብረት ላይ ጉዳት አልተፈጸመም፡፡ አንድም ባለስልጣን ማስፈራሪያ አልደረሰበትም ወይም ደግሞ የጥቃት ሰለባ አልሆነም፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ሴቶች ምንም ዓይነት የዘለፋ ቃላት እንኳ አልተጠቀሙም፡፡ ሁሉምን ነገር በሰላማዊ መንገድ፣ ሞገስን በተላበሰበ መልኩ እና በሚያስደምም ሁኔታ ነው ያከናወኑት፡፡ እነዚያ ጀግና ወጣት ሴቶች የምርጥ ተደናቂነት ተምሳሌት ቀንዲል ናቸው! በእነዚህ ወጣቶች እጅግ ኮርቻለሁ እናም ባርኔጣዬን ዝቅ በማድረግ አድናቆቴን ልገልጽላቸው እፈልጋለሁ፡፡

ነፃነት እንፈልጋለን ያሉ ሴት እህቶች በአደባባይ ተቃውሞ ካሰሙ በኋላ 6ቱ ወዲያው ታሰሩ  (የተቃውሞውን ቪድዮ ይዘናል)በዕለቱ የተከበረውን በዓል ኃላፊነት በመውሰድ ያዘጋጀው የገዥው አካል የሴቶች፣ የህጻናት እና ወጣቶች ሚኒስቴር ነበር፡፡ የገዥው አካል የዕለቱ መፈክር “የምርጥ ሴቶች የመጀመሪያው ዙር የ5 ኪ/ሜ ሩጫ“ የሚል ነበር (ምን ለማለት እንደተፈለገ ግልጽ ባይሆንም)፡፡ ገዥው አካል ዕለቱ ከ10,000 በላይ ሴቶችን እና ልጃገረዶችን ያሳትፋል በማለት ዲስኩር አድርጎ ነበር፡፡ ገዥው አካል በበዓሉ ዕለት ሴቶች እንዲሳተፉ በስፋት የጥሪ ማሳሰቢያ ሲያደርግ ጠንካራዎቹ የሰማያዊ ፓርቲ ሴት ወጣት አመራሮች ማሳሰቢያውን ሊሰሙት እንደሚችሉ እረስቶት ኖሯል፡፡ መንፈሰ ጠንካራዎቹ ወጣት ሴቶች ግን ማድረግ ያለባቸውን ነገር በሚያስደምም ሁኔታ አደረጉት፡፡ ወጣት ሴቶቹ ለገዥው አካል ፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ሳይሆን ብጫ ካናቴራ በመልበስ ተልዕኳቸውን ሲፈጽሙ ታይተዋል፡፡ እዚያ የተገኙት ለመሮጥ ነበር፣ ለነጻነታቸው ለመሮጥ፣ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ለመሮጥ፣ የኢትዮጵያ እስረኞች እንዲፈቱ ለመሮጥ፣ በመሰቃየት ላይ ላለው እና ተስፋ ለራቀው ህዝብ ትኩረት በመሳብ ለመሮጥ፡፡ ወጣቶቹ የሰማያዊ ፓርቲ ሴቶች አረመኒያዊ እና ጨካኝ እየተባለ በሚታወቀው ገዥው አካል ፊት ደፋርነታቸውን ማሳየት መቻላቸው ብቻ አይደለም አስደናቂ የሚሆነው ሆኖም ግን የእራሳቸውን የብልህነት ፈጠራ በመጠቀም የስርዓቱን ዕኩይ ምግባር በማጋለጣቸው ጭምር እንጅ፡፡

የአምስት ኪሎ ሜትሩ ሩጫ ከተጠናቀቀ በኋላ ሰባት የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶች በቁጥጥር ስር ውለዋል፣ ተደብድበዋል እንዲሁም ለእስር ተዳርገዋል፡፡ የሰብአዊ መብት እረገጣው ሰለባ ከሆኑት ውስጥ፡ ሜሮን ዓለማየሁ፣ ምኞቴ መኮንን፣ መታሰቢያ ተክሌ፣ ወይኒ ንጉሴ፣ ንግስት ወንድይፍራው፣ ወይንሸት ሞላ፣ እና እመቤት ግርማ ይገኙበታል፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ በከፍተኛ የስልጣን እርከን ላይ የሚገኙ ጌታነህ ባልቻ (የድርጅተ ጉዳይ ኃላፊ)፣ ብርሀኑ ተክለያሬድ (የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ) እና አቤል ኤፍሬም (የህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ አባል) የተባሉ ሌሎች ሶስት ወጣት ወንዶች ደግሞ እስረኛ ሴቶች ያሉበትን ሁኔታ ለመጠየቅ በሄዱ ጊዜ በቁጥጥር ስር ውለው እነርሱም ለእስር ተዳርገዋል፡፡

የጣይቱ እና የምኒልክ ልጆች በይስሙላው/በዝንጀሮዎች (ካንጋሩ ኮርት) ፍርድ ቤት፣

በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የይስሙላ ፍርድ ቤት ስርዓት በአገሪቷ ዘርግቶ በመተግበር ላይ ይገኛል በማለት ሁልጊዜ ስናገረው የቆየሁት ጉዳይ ነው፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ላይ የተመሰረቱት “ክሶች” የገዥው አካል የይስሙላ ፍርድ ቤቶች እንዴት ባለ ሁኔታ እየተካሄዱ እንዳሉ ከምንም ጥርጣሬ በላይ በግልጽ ያመላክታሉ፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ላይ የተመሰረቱት ክሶች በባዶው የትወና መድረክ ላይ ብቻ የሚከናወኑ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የይስሙላው ፍርድ ቤት እ.ኤ.አ ማርች 14/2014 ያደረገው የሁለተኛው ቀን “የችሎት” ትወና በሳሙኤል በኬት፣ ኢጀን ኔስኮ፣ ጂን ገነት ወይም ካፍካ ላይ የተደረገ ያለቀለት የትያትር ትወና ይመስል ነበር፡፡ የህጋዊነት ትወናው በምግባር የለሾች፣ በስም የለሾች፣ የማስተዋል ብቃት በሌላቸው፣ በህሊና የለሾች፣ በሀሳብ የለሽ ደነዞች፣ታማኝነት በሌላቸው ፖለቲከኞች እና ዋናው ተግባራቸው ህዝቡን ማሰቃየትን እና መከራ ማሳየትን እንደመርሀ የሚከተሉ አስመሳዮች በግልጽ በማይታይ መልኩ የሚጦዝ የውሸት የህጋዊነት ሽፋንን ተላብሶ እየተተገበረ ያለ ኃላፊት የጎደለው እና የተዋረደ የመድረክ ተውኔት ነው፡፡ ፍትህ ፊት የሌላት እና ቅርጿ የተበላሸ የይስሙላ ስርዓት ዘርግታ ትገኛለች፡፡ ፍትህ በሚያስገርም ሁኔታ በመደምሰሷ ምክንያት አካል የላትም፡፡ በኢትዮጵያ የፍትህ ፊት እና አካል በይስሙላው ፍርድ ቤት በርቀት በቁጥጥር ስልት መጠቀሚያ መሳሪያ ተይዞ የሚመራ እና በጌቶቹ ትዕዛዝ እንዲያደርግ የተሰጠውን ብቻ ያለምንም ኃፍረት ተቀብሎ እንደበቀቀን የሚደግም የሮቦት ዳኛ (አንደየተሞላ አሻንጉሊት) የተሰማራበት ሆኗል፡፡ የፍትህ አካሉ በዘራፊዎች ቁጥጥር ስር ዉሎአል፡፡

በ “ችሎቱ” ክፍል እንደ አንድ ተመልካች ዘገባ ከሆነ “የማታ” በሚል ስም የሚታወቅ “የፖሊስ መርማሪ” የሰማያዊ ፓርቲ ሴቶች የጣይቱ ልጆች ነን (የ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ንግስት የነበሩት) እና የእምዬ ምኒልክ ልጆች ነን (በ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ንጉስ እና የንግስት ጣይቱ ባለቤት የነበሩት) በማለት በአደባባይ በመጮህ በሽብር ተግባር ላይ ተዘፍቀው ታይተዋል በማለት የምስክርነት ቃሉን ሰጥቷል፡፡ “መርማሪው” በተጨማሪም ተከሳሾቹ እየተራቡ ያሉ መሆናቸውን እና የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ እንዲሁም በእስር ላይ የሚገኙት ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች ማለትም ርዕዮት፣ እስክንድር፣ አንዷለም እንዲሁም ሌሎች እንዲፈቱ” እያሉ በአደባባይ ጩኸት እያሰሙ ነበር ብሏል፡፡ እንግዲህ ይኸ ነው በሰማያዊ ፓርቲ ሴቶች ተፈጸመ የተባለው “የሽብር ተግባር” ይዘት፡፡

የችሎት ስነስርዓቱ ከታቀደለት በአንድ ሰዓት ዘግይቶ ነው የተጀመረው፣ ምክንያቱም የሰማያዊ ፓርቲ ሴቶች በሰልፉ ላይ ለብሰዋቸው የነበሩትን ካናቴራዎች ወደ ችሎቱ ሲቀርቡ እንዲቀይሯቸው ቢጠየቁም ለመቀየር ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ነበር፡፡ ፖሊሱ እስረኞቹን ከነካናቴራቸው ወደ ፍርድ ቤቱ እንዲቀርቡ መፍቀድ የፖለቲካ እምቢተኝነትን አምኖ እንደመቀበል ያስቆጥራል የሚል እምነት አደረበት፡፡ እንደ ዘገባው ከሆነ ሴቶቹ ወደ “ፍርድ ቤቱ” ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት የለበሷቸውን ካናቴራዎቻቸውን በማስገደድ እንዲቀይሩ ለማድረግ ፖሊ ሁከት ፈጥሮ እንደነበሩ ታውቋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶች እስከሚወሰዱ ድረስ በተያዙበት ቦታ እንዲቆዩ ተደርገዋል፡፡ “የፍርድ ቤቱ” ክፍል በተመልካች ተጨናንቋል፣ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችም በሙሉ ተገኝተው ነበር፡፡

የፌዴራል አቃቤ ህግ ጉዳዩን ለመመርመር እና መረጃ ለማሰባሰብ ተጨማሪ የ14 ቀናት ጊዜ እንዲሰጠው ሴት እስረኞችም በእስር እንዲቆዩ ጠየቀ፡፡ (በቁጥጥር ስር የማዋል ልምድ እና ተጠርጣሪን በእስር ቤት አውሎ ለጥፋተኝነት መረጃዎችን ለመፈለግ መሞከር የገዥው አካል የይስሙላው ፍርድ ቤት አሰራር ዋናው መለያ ባህሪው ነው፡፡ አንድ ተጠርጣሪ ፍርድ ቤት ከመቅረቡ በፊት የሚደረገው አሳፋሪ ዘዴ በእያንዳንዱ ከፍተኛ የወንጀል ጉዳይ ከሁለት ደርዘን ወይም ከዚያ በላይ በሚሆኑ በቀድሞዎቹ ባለስልጣኖች እና ባለፈው ዓመት ደግሞ በንግዱ ማህበረሰብ አባላት ላይ ሙስና በሚል ሰበብ የተደረገው እስራት ሲታይ ገዥው አካል ካለፉት አስርት ዓመታት በላይ ሲፈጽመው የቆየ ተግባር መሆኑን ነው፡፡ አቃቤ ህጉ እስከ አሁንም ድረስ ለሙስናው መረጃ ፍለጋ በሚል ሰበብ ጊዜ እየነጎደ በሄደ ቁጥር እነርሱ በእስር ቤት ተረስተዋል፣ ገዥው አካል ጉዳዩን ለሁለት ዓመታት ያህል ምርመራ እየተካሄደበት ነው በማለት በይፋ የገለጸ ቢሆንም)፡፡

የይስሙላ አቃቤ ህጉ ለሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የዋስትና መብት መሰጠት እንደሌለበት ተከራክሯል፣ ምክንያቱም “ዋስትናው ከተሰጠ አሁን በፖሊስ ቁጥጥር ስር ያሉት ታሳሪዎች መረጃዎችን ያጠፋሉ፣ እናም ምስክሮች የምስክርነት ቃላቸውን እንዳይሰጡ በማንገራገር እና በማስፈራራት እንዳይመሰክሩ ሊያደርጉ ይችላሉ” ብለዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ መከላከያ ጠበቃ አቶ ዓለሙ ጎቤቦ (በእስር ቤት የምትገኘው እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅናን ያተረፈችው ርዕዮት ዓለሙ አባት) ጉዳዩ የፖለቲካ ባህሪ ያለው ስለሆነ ልጆቹ የዋስትና መብታቸው ተጠብቆ ከውጭ ሆነው እንዲከራከሩ እንዲደረግ በማለት የክርክር ጭብጣቸውን አቅርበዋል፡፡ ቀጥለውም እንደ ህጉ ከሆነ ደንበኞቼ የዋስትና መብት እንዲያገኙ ይፈቅዳል፣ እናም ይህንን ላለማድረግ እየተከናወነ ያለው የዳኞቹ ተቃውሞ ተጠርጣሪዎቹን በእስር ቤት ለማማቀቅ የተደረገ ደባ ነው ብለዋል፡፡ “ዳኛው” የዋስትና ጥያቄውን አልተቀበሉትም፣ እናም የዳኝነት ሂደቱን ቀጠሉ፡፡ (ባለፉት በርካታ ከፍተኛ የሆኑ የፍርድ ቤት ጉዳዮች የፍርድ ሂደት ላይ እ.ኤ.አ የ2006 የቅንጅት ፓርቲ አመራሮችን “የፍርድ ሂደት” ጉዳይ ጨምሮ ገዥው አካል ምስክሮችን በማስፈራራት፣ ጉቦ በመስጠት፣ በሙስና አማልሎ ተጽዕኖ በማሳደር እና ከህግ አግባብ ውጭ በሆነ መልኩ ቃለመሃላን በመጣስ የውሸት የምስክርነት ቃል እንዲሰጡ በማድረግ ዕኩይ ምግባር ላይ ተዘፍቆ ይገኛል)፡፡

እንደ ፍርድ ቤት ተመልካች ታዛቢዎች ከሆነ የሰማያዊ ፓርቲ ሴቶች በእስር ቤቱ ውስጥ በቁጥጥር ስር ሆነው እያለ ከህግ አግባብ ውጭ በፖሊስ እና በደህንነት ኃላፊዎች አካላዊ ጉዳት እንደደረሰባቸው እንዲሁም የማስፈራራት ሰለባ እንዲሆኑ ጥረት እየተደረገ እንደሆነ ለይስሙላው ፍርድ ቤት ተናግረዋል፡፡ በሌሎች የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ላይ ቅጥረኛ እና ሰላይ እንዲሆኑ ብዙ ገንዘብ ቀርቦላቸዋል፡፡ ከተከሳሾቹ መካከል ትዕግስት ወንድይፍራው የተባለችው ባለፈው እኩለ ሌሊት ላይ ሶስት ወንድ ፖሊሶች እርሷ ወደታሰረችበት ክፍል መጥተው እንድትወጣ ትዕዛዝ እንደሰጧት “ለፍርድ ቤቱ” ተናግራለች፡፡ ከኃላፊዎች መካከል አንደኛው ዱላ በማንሳት በማወዛወዝ ካልተባበረች በስተቀር እስክትሞት ድረስ እንደሚደበድቧት ማስፈራራታቸውን ገልጻለች፡፡ ሌሎችም ሴቶች ተመሳሳይ የማስፈራሪያ ዛቻ እንደተፈጸመባቸው ተናግረዋል፡፡ ፖሊስ ሴቶቹ በሰማያዊ ፓርቲ ላይ የሚያደርጉትን ንቁ የአባልነት ተሳትፎ እና ጓዳዊ የትግል መንፈስ እንዲተው እና ከድጊታቸው እንዲታቀቡ በመደብደብ እንዳዋረዳቸው እና እንዳስፈራራቸው ያላቸውን ምሬት ገልጸዋል፡፡ በተመልካቾች ዕይታ “ብቃት የለሽ” ተብሎ የተፈረጀው የዕለቱ የችሎት ዳኛ ፖሊስ ምርመራውን አጠናቅቆ እ.ኤ.አ ለመጋቢት 18/2014 እንዲቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት አሰናብቷል፡፡

በይስሙላው ፍርድ ቤት ያለውን ኃይል መገዳደር፣

የሰማያዊ ፓርቲ ሴቶችን በቁጥጥር ስር የማዋል እና የፍርድ ሂደታቸው እንዲታይ ማድረግ እ.ኤ.አ በ2015 ይካሄዳል ተብሎ በሚታሰበው አገር አቀፋዊ ምርጫ ሰማያዊ ፓርቲ እንዳይሳተፍ እና ለመዝጋት በደጋኑ የተተኮሰ የመጀመሪያው ቀስት ነው፡፡ ገዥው አካል ለሰማያዊ ፓርቲ የሚያስተላልፈው መልዕክት ግልጽ እና ግድፈት ሊደረግበት የማይችል ሀቅ ነው፡፡ ይህም ሁኔታ በአንክሮ ሲታይ በቅርቡ ባረፉት በአቶ መለስ ዜናዊ የተጻፈው የባለ ሶስት ድርጊት የረዥም ጊዜ ተውኔት ተከታይ ነው፡፡ እነዚህ የተውኔት ድርጊቶችም እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡ ድርጊት አንድ፡ “ምርጫው” ከመድረሱ በፊት የሰማያዊ ፓርቲ, አመራሮችን እና አባላትን የይስሙላውን ፍርድ ቤቶች በመጠቀም ማሰቃየት፣ ማስፈራራት፣ ሽባ እና አቅመቢስ ማድረግ፡፡ በዚያ መንገድ ሌላ ተጨማሪ የኃይል እርምጃዎች ቢወሰዱ በህዝቡ ዘንድ የተለመደው አካሄድ እንጅ የበቀል እርምጃ አይደለም የሚል እንደምታ እንዲኖር ከመሻት የመነጨ ነው፡፡ ድርጊት ሁለት፡ ምርጫው ከመድረሱ ጥቂት ወራት በፊት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን እና አባላትን ሰብስቦ በእስር ቤት ማጎር፡፡ ይሄም የይስሙላውን ፍርድ ቤት አንደውነት የፍርድ ሸንጎ የሚሰራ ለማስመሰል ነው፡፡ ድርጊት ሶስት፡ ከምርጫ በኋላ እ.ኤ.አ በ2005 (1997 ምርጫ) የተደረገውን ጭፍጨፋ ድርጊት መድገም ነው፡፡!

የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን እና አባላትን የህግ ሂደት እና ጥቃት በተመለከተ ሁለት አማራጮች አሉ፡፡ 1ኛ) በይስሙላው ፍርድ ቤት የፍርድ ሂደት ላይ ተስፋ በመቁረጥ እራስን መነቅነቅ እና በመሰላቸት ጥሎ መሄድ 2ኛ) እንደ ኪልኬኔ አገር ድመቶች ከይስሙላው ፍርድ ቤት ጋር ጎሮሮ ለጉሮሮ መተናነቅ እና የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን እና አባላትን መብት ማስከበር፡፡

ገዥው አካል ኢትጵያውያን እና ሌሎች በይስሙላው ፍርድ ቤት የውሸት ማስመሰያ ምክንያት እራሳቸውን በመነቅነቅ ሁሉንም ነገር ይተውታል ወይም ደግሞ ትችት በመስጠት ብቻ ጥለው ይሄዳሉ የሚል እሳቤ ላይ የተንጠለጠለ ነው፡፡ ገዥው አካል በጊዜ ሂደት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችም እንደ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ አንዷለም አራጌ፣ አቡባከር አህመድ እና ሌሎችም በእስር ቤት ታጉረው “ይረሳሉ” የሚል ስሌት አለው፡፡ ገዥው አካል የይስሙላው የፍርድ ቤት ማስፈራሪያ ዘመቻ በከፍተኛ ውጤታማነት እና ብቃት ላይ ተመስርቶ የሚቀጥል ላለመሆኑ ትንሽም እንኳ ቢሆን ጥርጣሬ የለዉም፡፡

የሰላማዊ ትግል ዋና ዓላማው የጨቋኙን አካል ተቋማት እና ህጎች በመጠቀም በጨቋኙ አካል ላይ ትግሉን በሰላማዊ መልኩ በማፋፋም መቀጠል ነው፡፡ በአጠቃላይ መልኩ ሲታይ ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያለው ምንም ዓይነት የተፈጸመ ስህተት የለም፡፡ በገዥው አካል የይስሙላው ፍርድ ቤቶች ዘንድ የፍትህን ጥላ እንኳ ማግኘት እንደማይችል ማንም መገመት ይችላል፡፡ ማንም ቢሆን በውሸት እምነት ላይ በተመሰረተው የይስሙላው ፍርድ ቤት ፍትህ ሰበብ መሰቃየት የለበትም፡፡ ወደፊት ምን ሊከሰት እንደሚችል በእርግጠኝነት እናውቃለን፡፡ የክስ ሰነዱ ቀደም ሲል ተጽፎ ተዘጋጅቷል፣ በግልጽ ለመናገር ቀደም ሲል የነበረዉን የፖለቲካ ተቃዋሚዎች ክስ ስማቸውን በመለወጥ፣ በማደስ እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን በማካተት የክስ ሰነዶቹ እነዚህን ለመዳኘት በስራ ላይ ይውላሉ (በግልጽ አባባል ለማጥቂያነት ይውላሉ)፡፡

ያንን ትያትር ቀደም ሲል አይተነዋል፡፡ ክስ የቀረበባቸው የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች እና አባላት በየጥቂት ሳምንታት ልዩነት ከማጎሪያ እስር ቤቶች ወደ የይስሙላው ፍርድ ቤት እንዲመላለሱ ይደረጋል፡፡ የገዥው አካል አቃቤ ህግ ማስረጃ ለመፈለግ (የሩጫው ዕለት የተጠናቀቀ ስለሆነ እና ሌላ ተጨማሪ ማስረጃ ማግኘት የተሳሳተ እና ውኃ የሚቋጥር ባይሆንም) በሚል ስልት ብዙ የማዘግየት ስራዎችን በመስራት የተለመደውን የገዥውን አካል የበቀልተኝነት የሱስ ጥማት ለማርካት ጥረት ያደርጋል፡፡ የዋስትና መብት ጥያቄዎች ተከልክለዋል፣ ሺህ ጊዜ የሚጠየቁ ቢሆንም፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ሴቶች ይደበደባሉ፣ ህግወጥ አያያዝ ይፈጸምባቸዋል፣ እናም በእስር ቤት የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ይፈጸምባቸዋል፡፡ እርስ በእርሳቸው ላይ መተማመን እንዳይኖርም ጫና ይፈጸምባቸዋል፡፡ ህሊናቸውን እንዲሸጡ ገንዘብ እና ሌላ ሌላም ነገር ይሰጣቸዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲን ከፍተኛ አመራሮችን እንዲክዱ ላቅ ያለ ዋጋ የሚያወጡ ጌጣጌጦችን ይሰጧቸዋል፡፡ በጓደኞቻቸው፣ በፓርቲ አባላት እና አመራሮች እንዳይጎበኙ ክልከላ ሊጣል ይችላል፡፡ ለብቻ በአንድ ክፍል ውስጥ ሊታሰሩ ይችላሉ፡፡ የህክምና እርዳታ እንዳይደረግላቸው ክልከላ ሊደረግ ይችላል፡፡ በገዥው አካል በተቀጠረ ባለሙያ እንደተገለጸው እነዚህ እስረኞች “በሚከረፋው እስር ቤት” የገሀነም ህይወት እንዲገፉ ሊደረግ ይችላል፡፡ ይህ ጉዳይ ለብዙ ጊዜ ማለትም እ.ኤ.አ በ2015 እስከሚደረገው አገር አቀፍ “ምርጫ” ድረስ ቀጣይነት ሊኖረው ይችላል፡፡ ዘዴው ቀላል ነው፡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ሃሳብ ማስቀየስ፣ ማሸማቀቅ፣ ማስፈራራት፣ ከመሰረታዊ ዓላማቸው እንዲርቁ ማድረግ እና በአጠቃላይ መልኩ ደግሞ ምርጫ እየተባለ ከሚጠራው የይስሙላ ምርጫ ተሳትፏቸውን ሽባ ማድረግ ነው፡፡

ገዥው አካል የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ያለምንም ውይይት በፍጥነት ወደ እስር ቤት የመውሰዱን ሁኔታ በተመለከተ በእራሱ የይስሙላ ፍርድ ቤቶች ለምን ሊጠየቅ እና ሊሞገት እንደሚገባው አራት አሳማኝ ምክንያቶች አሉ፡፡ በመጀመሪያ የጅምላ ሰብአዊ መብት ረገጣው ተግባራዊ እንዲሆን የሚያግዙት የገዥው አካል ለጋሽ እና አበዳሪ ድርጅቶች (በተለይም የምራብ መንግሥታት) እነርሱ በሚያደርጉት ልገሳ ድርጊት እየተደረገ ያለውን የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ በተጨባጭ እንዲያዩት ይገደዳሉ፡፡ ለጋሽ እና አበዳሪ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እንዲስፋፋ እና ሰብአዊ መብት እንዲጠበቅ ደንታ አንደማይሰጣቸው የታወቀ ነው፡፡ ሁለተኛ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የይስሙላ የፍርድ ሂደት በእራሱ በይስሙላው ፍርድ ቤት ላይ አንዲፈረጅበት ማድረግ ያስፈለጋል፡፡ ገዥው አካል እራሱ ለይስሙላው የፍርድ ቤት ሂደት መቅረብ አለበት፡፡ ሶስተኛ የይስሙላው ፍርድ ቤት የፍርድ ሂደት ዛሬ በፍትህ ወንበር ላይ ተቀምጠው (እና ሌሎች ከመጋረጃ ጀርባ ተቀምጠው በዳኝት ወንበር ላይ የተሰየሙትን ዳኞች ጣቶች የሚጠመዝዙ) በእራሳቸው ዳኝነት ነገ እንደሚዳኙ በመገንዘብ ከፍተኛ ተቃውሞ መኖር አለበት፡፡ ዛሬ ከህግ አግባብ ውጭ ለመፍረድ በወንበር ላይ የተቀመጡት ሰዎች ከፍትህ ረዥም ክንድ ሊያመልጡ እንደማይችሉ የኑረምበርግ የፍርድ ሂደትን፣ የካምቦዲያ ፍርድ ቤት ልዩ የፍርድ ቤት ሂደትን፣ የሩዋንዳ የዓለም አቀፉን የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የፍርድ ሂደትን፣ የደቡብ አፍሪካ የእውነት እና የዕርቅ ኮሚሽንን፣ የቻርለስ ቴለር የዓለም አቀፉን የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የፍርድ ሂደትን እና የቦካሳን እና ሌሎች የአገር ውስጥ የፍርድ ሂደቶች ሊያስታውሱ ይገባል፡፡ ሁኔታዎች ሁልጊዜ ይገለባበጣሉ፡፡ ስለ ሁኔታዎች መገለባበጥ ጉዳይ እስቲ ደጋግማችሁ አስቡ፡፡ ሁልጊዜ ይገለባበጣሉ!

ከደቡብ አፍሪካ ታሪክ ብዙ ቁም ነገሮችን ልንማር እንችላለን፡፡ እ.ኤ.አ በ1964 የአፓርታይድ ገዥ አካል የአፍሪካ ኮንግረስ መሪዎችን እና ሌሎች የጸረ አፓርታይድ ተሟጋቾችን ኔልሰን ማንዴላን፣ ዋልተር ሲሱሉ፣ ጎቫን ኢምቤኪ፣ ራይሞንድ ሃላባ፣ አህመድ ካትራዳ፣ ኤሊያስ ሞሶሌዲ እና ቢሊ ኔይር ሰብስቦ በይስሙላው የአፓርታይድ የፍትህ ችሎት ፊት ገተራቸው፡፡ እነዚህ ሰባት አመራሮች እንደ “ጣይቱ ሰባት” የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ሁሉ በአፓርታይድ የይስሙላ ፍርድ ቤቶች ፍትህን እናገኛለን የሚል እምነት አልነበራቸውም፡፡ ሆኖም ግን መሰረተ ቢስ ክሱን አጥብቀው ተቃውመውታል፡፡ ይህንንም በማድረጋቸው ለደቡብ አፍሪካ ብቻ ሳይሆን ለጠቅላላው ዓለም ታሪክ ሰርተዋል፡፡ የሰባቱ የጸረ አፓርታይድ መሪዎች የሪቮኒያ የፍርድ ሂደት ለዛሬዋ ደቡብ አፍሪካ ፍትህ መስፈን መሰረትን የጣለ ነው፡፡

አራተኛው እና ምናልባትም በጣም ጠቃሚው ነገር የይስሙላውን ፍርድ ቤት አጥብቀን መዋጋት አስፈላጊ ነው ምክንያቱም በህግ የበላይነት ለሚያምኑ ሁሉ ለህጉ ተገዥ ላልሆኑት ወንጀለኞች የህይወት እና የመተንፈስን ያህል ጠቃሚ መሆናቸውን ሊያስተምሩ የሚችሉበት ብቸኛው መንገድ ነው፡፡ በህግ የበላይነት ላይ እምነት ያላቸው ሰዎች ብቻ ናቸው ስለወንጀለኞች ማስተማር እና መጮህ ያለባቸው፡፡ እራሱ ያወጣቸውን እና ያጸደቃቸውን ህጎች የሚደፈጥጥ ወሮበላ መንግስት በእራሱ እና በህግ የበላይነት ላይ ንቀትን የሚፈለፍል ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የህግ የበላይነትን ለመያዝ እና ለመንከባከብ ከማንም የተሻለ መሆን አለበት፡፡

“የጣይቱ ሰባት የህግ ጥበቃ ፈንድን (ድጎማ/ዝክር)” እንደግፍ፣

Semayawi Party Legal Defense Fund 2ሁሉንም አንባቢዎቼን “ለጣይቱ ሰባት የህግ ጥበቃ ፈንድ (ድጎማ/ዝክር)” እንድታዋጡ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡ የሰኞ ትችት መጣጥፌን ለበርካታ ዓመታት ስታነቡ የቆያችሁ በርካታ ወገኖቼ እንዳላችሁ እገነዘባለሁ፡፡ የሰኞ ትችት መጣጥፌ አሁን ስምንተኛ ዓመቱ መሆኑ ነው፡፡ አንዳንዶች ከእኔ ጋር በሁሉም ነገር በሀሳብ የማይግባቡ እንዳሉ አውቃለሁ፡፡ እንደዚሁም በርካታ ለመቁጠር የሚያስቸግር ብዛት ያላቸው አንባቢዎቼ ደግሞ ቢያንስ በጥቂት ነገሮች ላይ ከእኔ ሀሳብ ጋር እንደሚስማሙ እገነዘባለሁ፡፡ የእኔ አቤቱታ የቀረበው ለእነዚህኛዎቹ ወገኖቼ ነው፡፡ በኢትዮጵያ በገዥው አካል የይስሙላው ፍርድ ቤት የፍርድ ሂደት እየተሰቃዩ ያሉትን “የጣይቱ ሰባት” ጀግኖችን በመርዳቱ ጥረት እያንዳንዳቸው ማገዝ እንዲችሉ ያቀረብኩትን ሀሳብ በመደገፍ በተግባር እንዲያሳዩ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡ እርዳታ እንዲያደርጉም በአጽንኦ እማጸናለሁ፡፡ ምንም ትንሽም ቢሆንም እንኳን ስጋት አይደርባችሁ፣ ትልቅ ጋን በትንሽ ጠጠር ይደገፋል ነውና፡፡ ባለፉት ዓመታት ምን ለመስራት እንዳቀድኩ አድናቆታቸውን የገለጹልኝ በርካታ ኢትዮጵያዊያን/ት ወገኖቼን በተለያዩ ጊዚያት አግኝቸ ነበር፡፡ ምንም ይሁን ምን ለሰራሁት ሁሉ ምስጋናን አልሻም፣ በኢትዮጵያ ያለው የሰብአዊ መብት ያለመሻሻል ሁኔታን ስመለከት ካሁን የበለጠ ሺ አጥፍ መሆን የሆነ ስራ መስራት ነበረብኝ በማለት አራሴን ወቅሳለሁ፡፡

የዛሬ ሰባት ዓመት በዚሁ ወር “ትንሿ ወፍ እና የጫካው እሳት: የዲያስፖራው ማህበረሰብ የሞራል ትረካ” በሚል ርዕስ ስር በትችት መጣጥፌ ላይ ምን ለመስራት እንዳሰብኩ ለአንባቢዎቼ ተናግሬ ነበር፡፡ በዚህም መሰረት ማድረግ የምችለውን ሁሉ እያደረግሁ ነው፡፡ አሁን አንባቢዎቼን መጠየቅ የምፈልገው ማድረግ የሚችሉትን ሁሉ እንዲያደርጉ ነው፡፡ እስቲ በጥሞና አስቡት ወገኖቼ በመቶዎች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ትናንሽ ወፎች አንድ ላይ ተባብረው በመስራት የጫካን እሳት መግታት ይችላሉ፡፡ በአሁኑ ጊዜ የ”ጣይቱ ሰባት” ጀግኖች በአረመኔው ገዥ አካል የእሳት ማቀጣጠያ ጉድጓድ ውስጥ ናቸው፡፡ ሲቃጠሉ መመልከት አለብን ወይም ደግሞ ከእነርሱ ጎን በመቆም ታግለን ለድል መብቃት አለብን፡፡ “ለጣይቱ ሰባት የህግ ጥበቃ ፈንድ(ድጎማ/ዝክር)” እርዳታችሁን እንድታደርጉ እማጸናለሁ፡፡ ለወደፊቱ የኢትዮጵያ ወጣት ወንዶች እና ሴቶች ተቆርቋሪነታችሁን አሁኑኑ በተግባር አሳዩ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲን ሴት ጠይቁ…

Free the Taitu Seven Amharicከቀድሞዋ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ማጊ ታቼር ጋር በብዙ ነገሮች ላይ እንደማልስማማ አምናለሁ፡፡ ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትሯ በሴቶች የፖለቲካ አመለካከት ላይ በነበራቸው እምነት ምንም ዓይነት ያለመስማማት አዝማሚያ አልነበረኝም፡፡ “በፖለቲካው ዓለም የተነገረ ምንም ነገር በፈለጋችሁ ቁጥር ወንድን ጠይቁ፡፡ የተሰራ ምንም ነገር በፈለጋችሁ ጊዜ ግን ሴትን ጠይቁ“ ነበር ያሉት፡፡ ሰለሆነም ለእነዚህ ወጣት ሴት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች እና አባላት አንድ ነገር እናድርግ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ሴቶች እሩጡ፣ እሩጡ…! ለነጻነት የምታደርጉትን ሩጫ በጽናት ቀጥሉበት…

በዚህ ድረ ገጽ የእርዳታ እጃችሁን ለምትዘረጉ: http://www.semayawiusa.org/donate/

በባንክ ሐዋላ ለመርዳት ለምትፈልጉ፡

ለሰሜን አሜሪካ የሰማያዊ ድጋፍ የሚከፈል (የአሜሪካ ባንክ (Bank of America)

የሂሳብ ቁጥር፡ 435031829977

የመላኪያ ቁጥር፡ 051000017

በቼክ ለመርዳት ለምትፈልጉ፡

ለሰሜን አሜሪካ የሰማያዊ ድጋፍ የሚከፈል

የ.ፖ ሳ.ቁ 75860

ዋሽንግተን ዲሲ. 20013

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

መጋቢት 9 ቀን 2006 ዓ.ም.

Health: ከደባሪ ህይወት እና ስሜት ተላቆ ደስተኛ ሆኖ ለመኖር የሚያስችሉ 6 ጥበቦች

0
0

happy life
6
ያለፈውን ነገር እንደገና መመለስ እንደማትችል እወቅና ተቀበል

በተገቢው ጊዜ ተገቢ ስራ ባለመስራትህ ተሳስተሃል፡፡ ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ ሀዘንህን ግለፅ፡፡ ‹‹ወይኔ›› ብለህ አልቅስና ይውጣልህ፡፡ ይህ ያለፈውን ስህተት ለመቅበር ይረዳሃል፡፡ ስላለፈው ህይወትህ ስታስብ በየጊዜው ሐዘን፣ ድብርትና ተስፋቢስነት እንዳይሰማህ ያግዝሃል፡፡

5
ነገ በአንተ አዲስ ቀን መሆኑን እመን

38 ዓመት ምናልባት በከንቱ አልፏል፡፡ ሆኖም ግን ይህ ለአንተ የህይወትህ መጨረሻ አይደለም፡፡ የአማካይ ሰው ዕድሜ ብንወስድ እንኳ ገና ብዙ ዓመታት አሉህ (56-38)፡፡ ስለዚህ ለውጥ በማምጣት በአዲስ የህይወት ጎዳና ላይ መራመድ ትችላለህ፡፡ አሁን በመጣልህ ማስተዋል ተጠቅመህ የዛሬውን/የነገውን ሕይወትህን መለወጥ እንደምትችል እመን፡፡
rules-of-happy-life
ትኩረትህ በትናንት ላይ ሳይሆን በነገ ላይ ይሁን፡፡ ያለፈውን የህይወት ዘመንህን ቆርጠህ መጣል አትችልም፤ የህይወትህ ታሪክ ነው፡፡ ሆኖም አቅጣጫህን ወደ ኋላ ሳይሆን ወደ ፊት ማድረግ ትችላለህ፡፡ በአዕምሮህ ነገን/ወደፊትን ከተመለከትህ ትናንት ከአንተ ኋላ ይሆናል፤ በአዕምሮህ ትናንትን የምትመለከት ከሆነ ደግሞ ፊትህ ወደ ትናንት ጀርባህ ደግሞ ወደ ነገ ይሆናል፡፡ አንተ ትናንትን በማሰብ ሳይሆን ነገን በማሰብ ደስተኛ ልትሆን ትችላለህ፡፡ በትናንትህ ውስጥ የሚታጨድ መልካም ነገር የለም፤ በነገ ውስጥ ግን ደስታን ሊያመጣ የሚችል ተስፋ አለ፡፡ ትናንት ጨለማ ነው፤ በነገ ውስጥ ግን የህይወት ብርሃን ተስፋ ይኖራል፡፡ ስለዚህ ‹‹ከእኔ ትናንት ይልቅ የእኔ ነገ ተስፋ አለው›› የሚል እይታ ይኑርህ!

4
ተስፋ ሳትቆጥ አዎንታዊ እርምጃ ውሰድ

ከዚህ ከሚደብርህ ህይወት ለመላቀቅ አይነተኛው መንገድ የአንተ ለለውጥ ለመስራት ያለህ ቁርጠኝነት ነው፡፡ የምትፈልገው ግብ (የግል ደህና ገቢ ያለውን ስራ መያዝ) ሩቅ ሊመስልህ ይችላል፤ በእርግጥ ሊሆንም ይችላል፡፡ ሆኖም በርትተህ በአንድ ጊዜ አንድ እርምጃ ከወሰድክ በረጅም ርቀት ያሰብከው ቦታ ትደርሳለህ፡፡ ከዚህ በላይ በየዕለቱ የምትወስዳቸው መልካም እርምጃዎች እያስደሰቱህ ይመጣሉ፡፡ ሌላው ደግሞ የግል ደህና ገቢ ያለው ስራ መሆኑን እንጂ ስራው ምን አይነት እንደሆነ፣ ይህን ስራ ለመስራት አሁን በእጅህ ያለው ግብአት (ዕውቀት፣ ገንዘብ፣ ምቹ ሁኔታዎች ወዘተ) መለየት እንዲሁም ከግብ የሚያደርስን ተጨባጭ ስልት ማውጣት ጠቃሚ ነው፡፡ ተገባራዊ እርምጃ ካልወሰድክ ግን መልካም ሐሳብህን በክፉ ሐሳብ ገደልከው ማለት ነው፡፡ ‹‹የአንድ ሺ ኪሎ ሜትር መንገድ በአንድ እርምጃ ይጀምራል›› የሚባለውን አባባል ሰምተህ ይሆናል፡፡ በቀሪው ህይወትህ ጠንክረህ በትጋት ከሰራህ ለውጥ ታመጣለህ፤ ካልሆነ ግን ይህም ጊዜ እንደ ወጣትነቱ ጊዜ ምንም ስራ ሳይሰራበት ያልፍና እውነተኛ ጨርቅ ጥሎ መብረር ሊከሰት ይችላል፡፡

3
አዎንታዊ እይታን አጎልብት

አሁን ያለው አስታሰብህ/እይታህ አሉታዊ ይመስላል፡፡ ‹‹ይህ ነው የሚባለው ምንም ዋጋ ያለው ነገር በህይወቴ እንደሰራሁ አይሰማኝም›› የሚለው ሀሳብ አሉታዊ ነው፡፡ ከአንተ ተጨባጭ እውነታ አንፃር ይህ እውነታ ቢሆንም፣ በህይወትህ መልካምና ጠንካራ ነገሮችም ይኖራሉ ብዬ አስባለሁ፡፡ ያለውን ነባራዊ እውነታ መቀበል አንድ ነገር ሆኖ በአሉታዊ እይታ መሞላት ግን የተለየ ነው፡፡ ‹‹እኔ ዜሮ ነኝ›› የሚለው ሐሳብ ራስን ወደ መኮነን፣ ከዚያም ወደ ድብርት/የመንፈስ መውደቅ፣ ሲበዛ ደግሞ ራስንም ለማጥፋት ወደማሰብ ሊያመራ ስለሚችል አዕምሮህን ከአሉታዊ አስተሳሰብ ለመጠበቅ ሞክር፡፡ ለምሳሌ አንተ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት ዲፕሎማ አለህ፤ ከሰዎች ጋር ደግሞ ተግባቢ ትመስላለህ (ጨዋታ አዋቂ አይነት ነኝ ብለሃል)፣ አሁን የዕለት ተዕለት ወጪህን የሚሸፍን የገቢ ምንጭ አለህ… ስለዚህ ባዶ አይደለህም፡፡

2
ራስህን ከሌሎች ጋር ማወዳደርህን ተው

በተለይ የአንተ ጓደኞች በወጣትነታቸው ጊዜ ተገቢውን ስራ በመስራታቸው አሁን መልካም ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡ አንተ አሁን በቀሪው ዘመንህ የቻልከውን ያህል በመሮጥ አሁን ካለህበት ወደ ፊት ፈቀቅ ማለቱ በቂ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ የሚያዋጣህ ከዚህ በኋላ የምትሰራቸውንና ውጤቱን ቀድሞ ከነበረህ ህይወት ጋር ማነፃፀር እንጂ ከሌሎች ሰዎች ጋር ራስህን ማወዳደር ራስህን አሳንሰህ እንድትመለከት ያደርግሃል፡፡

1
ፍቅርና ትዳርን ማሰብ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል

የትዳርም ሆነ የፍቅር አጋር እንደሌለህ ተናግረሃል፡፡ ይህ በምርጫ/በውሳኔ ነው ወይስ ባለመሳካቱ ነው? አሁን የቀድሞ ጓደኞችህ ከአንተ ጋር የሉም፤ ወላጆችህም እስከ መጨረሻ ከአንተ ጋር አይኖሩም፡፡ (አሁን በህይወት ካሉ) ስለዚህ የኑሮ አጋር መፈለግ በኑሮም ሆነ በስሜት ለመደገፍ ጥቅም አለው፡፡

[ሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ] “ለቤተክርስቲያናችን ሰላምና አንድነት ስንል ዝም አንልም”–ለቤ/ክ ሰላምና አንድነት ከቆሙ ምዕመናን

0
0

debereselam Minnesota
3/19/2014
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ፤ አሜን !

ለቤተክርስቲያናችን ሰላምና አንድነት ስንል ዝም አንልም።
ለቤተክርስቲያን ሰላምና አንድነት ከቆሙ ምዕመናን።

ቤተክርስቲያናችን ደብረሰላም መድኃኔዓለም በይፋ ከተምሠረተችበት ከ 1994 ዓ.ም እ.ኤ.አ ጀምሮ በብዙህ ሺህ ለሚቆጠሩ ስደተኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች እጅግ በርካታ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶችን ስትሰጥ ቆይታለች፤አሁንም በመስጠት ላይ ትገኛለች። የቤተክርስቲያን ሕይወትና ጉዞ ግን ቀላልና አልጋ በአልጋ ስላልሆነ በየጊዜው ብዙ ፈተናዎች ያጋጥማሉ። የዚህ የዛሬው መልዕክት ዋና አላማም በቤትክርስቲያናችን ጉዞ ውስጥ አንዱና ትልቁ የሆነውን በአሁኑ ሰዓት ያጋጠመንን ፈተና ከሥር ከመሠረቱ ለሁሉም ለማሳወቅ ነው።

ሁላችሁም እንደምታውቁት ቤተክርስቲያናችን ደብረሰላም ፍጹም የኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት፣ ቀኖና፣ትምሕርትና ትውፊት የሚፈጸምባት ብቻ ሳትሆን የሚሰጠው አገልግሎትም በኢትዮጵያ ካሉ ታላላቅ አድባራትና ገዳማት ጋር የሚተካከልና ዝናዋም በመላው ዓለም የገነነ ነው። ይህች ቤተክርስቲያን ገና ሥትመሰረት ጀምሮ በገለልተኛ አስተዳደር እንድትመራ በወቅቱ የነበሩ መሥራች አባላት ተስማምተው ያደረጉት እንደሆነ ሁሉም የሚመሰክሩት ነው። ይህም የሆነበት ዋናው ምክንያት በወቅቱ በሥልጣን ላይ የነበሩት ፓትርያርክ በመንግሥት ጣልቃ ገብነት ተነስተዋል በሚልና የተሾሙትም አባት የመንግሥት ብርቱ ደጋፊ እንደነበሩ ይነገር ስለነበረ በተጨማሪም በምዕራቡ ዓለም ለረጅም ጊዜ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ ክ ሊቀ ጳጳስ ሆነው ያገለገሉት አባት (አቡነ ይስሐቅ) የፕትርክና ሹም ሽሩን ድርጊት በመቃወማቸው ቤተክርስቲያኗ ከየትኛውም አስተዳደር ሳትወግን በአስተዳደር ገለልተኛ ሆና በሜኖሶታ የቤተክርስቲያናት ማቋቋሚያ ሕግ እንድትተዳደርና ለውስጥ አሰራርም መተዳደሪያ ደንብ እንዲዘጋጅ ተደርጓል።

በተግባርና በመረጃ እንደታየውም በኢትዮጵያ በሥልጣን ላይ የተቀመጡት አባት በርግጥም የመንግሥት ጉዳይ አስፈጻሚ እንጂ ለቤተክርስቲያንና ለምእመናንን ብዙም ደንታ የነበራችው ስላልነበሩ፤ ከስልጣን የተባረሩት አባትም በወቅቱ እንደተባለው በህመም አለመሆኑና በመንግሥት ትእዛዝ እንደተነሱ መረጃዎች በመውጣታቸው በአንዲት ቤተክርስቲያን ሁለት ፓትርያርክና ሁለት አመራር ሊኖር አይገባም የተለያዩት አባቶች አንድ እስኪሆኑና አንድ አመራር እስኪሆን ድረስ ቤተክርስቲያኗ በገለልተኝነት አቋማ እንድትቀጥል ሆኗል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ይህ የመለያየት መንስዔ ሳይፈታና ምንም ዓይነት ለውጥ ሳያሳይ ከተስፋ መቁረጥና ከእምነት ጽናት ማነስ በመነጨ ይህን የገለልተኝነት አቋም ለመቀየርና ኢትዮጵያ ካሉት አባቶች/ሲኖዶስ ጋር የመቀላቀል ጥያቄ በሰንበት ት/ቤት በቀረበ። በጥያቄውም መነሻነት ጁን 2 ቀን 2013 ዓ.ም በተደረገው የአባላት ጠቅላላ ጉባዔ አብዛኛው የቤተክርስቲያኗ አባላት ቤተክርስቲያናችን ባለችበት አቋሟ እንድትቀጥል የሚፈልጉ መሆናቸውን ባቀረቧቸው አስተያየቶችና የውሳኔ ሐሳብ ቢገልጹም በቤተክርስቲያኗ ተቀዳሚ ካሕን ውግዘት መስይ ቃል ውሳኔ ሳይሰጥ ጉዳዩ በይደር ተይዞ የበለጠ ግንዛቤ እንዲኖር በሚል በፓናል ውይይት እንዲቀርብ ተደረገ። ዲሴምበር 15 ቀን 2013 ዓ.ም በተደረገው የፓናል ውይይት ላይ ባለንበት እንቆይ በሚለው እና ኢትዮጵያ ባለው ሲኖዶስ እንተዳደር በሚለው ሃሳብ የተዘጋጁት ቡድኖች ከጉዳዩ ጋር ይገናኛል ብለው ያመኑበትን ጥናት በጽሑፍ ካቀረቡና ለተለያዩ
ጥያቄዎችም ማብራሪያዎች ከተሰጡ በኋላ( ለ6 ሰዓት የቆየ ስብሰባ ነበር) አባላት ድምጽ እንዲሰጡበት ተደርጎ በስብሰባው ተካፋይ ከሆኑት አባላት ከፈተኛ ቁጥር ያላቸው ቤተክርስቲያኗ ባለችበት የአስተዳደር ገለልተኝነት አቋም እንድትቀጥል ወስነዋል።

ይህንንም ውሳኔ ተከትሎ በተደረጉ የአስተዳደር ቦርድ ስብሰባዎች ላይ አንዳንድ የአስተዳደር ቦርድ አባላት በወቅቱ የስብሰባው ምልዐተ ጉባዔ/ኮረም/ ስላልሞላ ውሳኔውን አንቀበልም በማለታቸውና በተቃራኒው ደግሞ የአስተዳደር ሊቀመንበሩና ሌሎች የቦርድ አባላት የኅዝብን ውሳኔ ማክበር ይገባናል ውሳኔን የመሻር መብት ያለው ጠቅላላ ጉባዔ ብቻ ነው ሲሉ የተለያየ አቋም በመያዛቸው በአስተዳደር ቦርዱ አባላት መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ሊቀመንበሩ ጉዳዩን ባለቤቱ ኅዝቡ ተመልክቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት አጠቃላይ የስብሰባ ጥሪ ለፌብረዋሪ 16 2014 ጠሩ። ነግር ግን የኅዝቡን ውሳኔ መቀበል ያልፈለጉት የአስተዳደር ቦርድ አባላቱ ጄንዋሪ 23 2014 ባደረጉት ህገወጥ ስብሰባ ሊቀመንበሩን ከሥልጣናቸው አውርደናል ሲሉ ተናገሩ። መጀምሪያ ግን ይህ ሊቀመንበሩ ከሥልጣናቸው ወርደዋል የሚለው ትእዛዝ የመጣው ‘የቤተክርስቲያኑ ጠብቃ ነኝ’ ከምትል አንዲት የሕግ ባለሙያ ሴት ነው። ለዚህች ሴት ማን ቤተክርስቲያኑን እንድትወክል ውል እንደፈረመላት ባይታወቅም የተቀጠረችው በግለሰቦችና በአንዳንድ የቦርድ አባላት እንደሆነ ይነገራል። በቤተክርስቲያናችን መተዳደሪያ ደንብ መሰረት ቤተክርስቲያኑን ወክሎ ማናቸውንም ሰነድ የሚፈርመው ሊቀመንበሩ ብቻ እንደሆነ በአንቀጽ 6 ክፍል 3 ‘ሀ’ 7) ላይ ተደንግጓል። እዚህ ላይ ልብ ሊሉት የሚገባው ነገር ሊቀመንበሩን አውርደናል ባሉበትና ሌላም ባልተሾመበት ሁኔታ ማን በቤተክርስቲያኑ ስም ውል እንደፈረመ ነው። አሁንም ይህ ጠበቃ ለቤተክርስቲያኑ ቀጥረናል ተብሎ የተላለፈው መልእክት ግልጽ አይደለም።

ሊቀመንበሩን ከሥልጣናቸው ለጊዜው አግዶ ለጠቅላላ ጉባዔ ማቅረብ የሚቻልበት የውስጥ አሰራር እያለ ለምን ጠበቃ መቅጠርና ከፍተኛ ወጪ ማስክተል አስፈለገ? ይህ አላስፈላጊ አካሔድ ያሳሰባችው የቦርድ አባላት ሊከተል የሚችለውን ከፍተኛ ወጪ ለማስቆምና የቤተክርስቲያኑን ገንዘብ ለማስጠበቅ ሲሉ የእገዳ ይጣልልን አቤቱታ ለፍርድ ቤት አቅርበዋል።

ስለሆነም እነኝህ ያለአግባብ እየሔዱ ያሉ የቦርድ አባላት የቤተክርስቲያናችንን ሊቀመንበር አውርደናል ካሉ በኋላ የቤተክርስቲያኑን ንብረትና ገንዘብ ለመጠበቅ ሲባል እንዲሁም እየተከሉት ያለውን ከመተዳደሪያ ደንቡና ከስቴቱ የቤተክርስቲያናት ሕግ ወጪ የሆነ አካሔድ ለማስቆም ሲባል ከፍርድ ቤት አስቸኳይ የእገዳ ማዘዣ ለማውጣት የተወሰደውን ርምጃ ነው ቤተክርስቲያኑ ተከሷል በማለት ሕዝቡን ለማደናገር እሞከሩ ያሉት። እውነታው ግን ሕዝቡ ተሰብስቦ በተከሰተው ጉዳይ ላይ ተነጋግሮ ውሳኔ እንዳይሰጥ እንቅፋት የሆኑት እነኝሁ የሕዝቡን ውሳኔ አንቀበልም በማለት ቤተክርስቲያናችንን አሳልፈው ለመስጠት ሁሉንም ሕገ-ወጥ አሰራር እየገፉበት ያሉት የቦርድ አባላት ናቸው። ከጄነዋሪ 11/ 2014 የአስተዳደር ቦርድ ስብሰባ በኋላ ምንም አይነት የአስተዳደር ቦርድ ስብሰባ ተደርጎ አያውቅም። በዚህ ሁኔታ ቤተክርስቲያኑ ተከሷል ጠበቃ ገዝተናል እንዴት ሊባል እንደተቻለም ግራ የሚያጋባ ነው።
ከአራት መቶ በላይ የሚሆን ህዝብ ፔትሺን ፈርሞ አጠቃላይ የአባላት ስብሰባ እንዲደረግ ቢጠይቅም በተጨማሪም ፍርድ ቤቱ ፌብረዋሪ 5 2014 ጉዳያችሁን በጠቅላላ ስብሰባ ፍቱትና አስታውቁኝ በማልት ማሳሰቢያ ቢሰጥም አሻፈረኝ በማለት ያለሕዝቡ ፈቃድና እውቅና ጠበቃ በመቅጠር ከፍተኛ ወጪ ስለተጠየቀ ይህንንም ከፍተኛ ወጪ ከቤተክርስቲያኑ አካውንት የሚያውጡበት አሰራርና ሕግም ስለሌለ ሕዝቡን ‘ቤተክርስቲያናችን ተከሰሰ’ በማለት ከእውነታው የራቀ ውዥንብር አሰራጭተዋል። ለመሆኑ ቤተክርስቲያኑ በምን ጉዳይ ላይ ነው የተከሰሰው??? በወንጄል ነው በፍታብሔር ??? ቤተክርስቲያኑ ማንን ምን ስላደረገ ነው የተከሰሰው ??? ማነውስ የራሱን ቤተክርስቲያን የሚከሰው ???

ከላይ እንደተጠቀሰው የሕዝቡን ውሳኔ አንቀበልም ያሉ የቦርድ አባላት በቤተክርስቲያኑ ገንዘብ ላይ ብክነት እንዳያስከትሉና ያለሕዝቡ ፈቃድ ወደ ኢትዮጵያው ሲኖዶስ ተቀላቅሏል እንዳይሉ የእገዳ ማእቀብ ይደረግን የሚል ጥያቄ ብቻ ነው ለፍርድ ቤት የቀረበው። ይህም ጥያቄ የአራት የቦርድ አባላት ብቻ ሳይሆን ከአራት መቶ በላይ የሆኑ አባላት ፔትሺን የፈረሙበት ጉዳይ ነው። አሁንም በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሕዝቡ ባስቸኳይ ተሰብስቦ በቦርዱ አባላትም ሆነ በማንኛውም ጉዳይ ላይ ውሳኔውን እንዲያሳልፍ የሽምግልና ሒደት/mediation/ እየተከናወነ ሲሆን አሉ የሚባሉ ጉዳዮችን ሁሉ ለሕዝቡ በጠቅላላ ጉባዔ ላይ መግለጽ እየተቻለ ሕዝብን ለማሸበርና ያልተደረገውን ተደርጓል ተብሎ የተላለፈው መልእክት ውሸት መሆኑን ሁሉም እንዲያውቀው እንወዳለን።

በመጨረሻም የሁሉም ጉዳይ ባለቤትና የመጨረሻ ውሳኔ ሰጪ የአባላት ጠቅላላ ጉባዔ ስለሆነ የአባላት ጠቅላላ ጉባዔ በቀረቡት ፔትሺኖች መሠረት ባስቸኳይ እንዲጠራ እናሳስባለን።

መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያናችንን በሰላምና በአንድነቷ ያጽናልን። አሜን!

የመብራት መቆራረጥ ያማረረው የአዲስ አበባ የሽሮሜዳ አካባቢ ነዋሪ ሰልፍ ወጣ

0
0

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)


በአዲስ አበባ የሚሰራጨው ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራድዮ እንደዘገበው የመብራት መቆራረጥ ያማረረው በአዲስ አበባ የሽሮሜዳ አካባቢ ነዋሪዎች ሰልፍ ወጡ።

ራድዮው እንዳነጋገራቸው ነዋሪዎች ገለጻ በአካባቢው የሚኖረው ሕዝብ በተደጋጋሚ ለሚመለከተው አካል ስሞታ ቢያቀርቡም መፍትሄ ባለማግኘታቸው ስልፍ ለመውጣት ምክንያት ሆኗቸዋል። ሰልፈኞቹ በተደጋጋሚ የሚያጋጥመውን እና ብልጭ ድርግም ከማለት ጀምሮ ለቀናት ጭራሹኑ እስከመጥፋት በሚደርሰው የኤሌክትሪክ ሃይል መማረራቸውን ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በመገኘት ነው በተቃውሞ ሰልፍ ድምጻቸውን ሲያሰሙ ውለዋል ያለው ራድዮ ጣቢያው የሚመለከታቸውን የስራ ሃላፊዎች በማግኘት ምላሻቸውን ለመስማት የተደረገው ጥረት አልተሳካልኝም ሲል ዘግቧል።

በሌላ በኩል በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥን በመማረር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የተለያዩ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ድምጻቸውን ለማሰማት የወጡ ሰልፈኞች ምላሸ ሳይሰጣቸው “ተበተኑ” በሚል ትእዛዝ እንዲበተኑ እንደሚደረግ ሸገር የዘገበ ሲሆን የሽሮሜዳ አካባቢ ነዋሪዎችም የሬድዮ ጣቢያው ጋዜጠኞች በቦታው ከመድረሳቸው በፊት እንዲበተኑ መደረጉን ነው አስታውቋል።

በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የትራንስፖርት፣ የውሃ፣ የመብራት፣ የቴሌኮምዩኒኬሽን፣ የጋዝ እና የሌሎችም እጥረቶች ሕዝቡን እያማረሩት ከእለት ተእለት እንቅስቃሴው እየገደቡት ይገኛሉ።

የታክሲ ወረፋ በአዲስ አበባ

የታክሲ ወረፋ በአዲስ አበባ


አባ መላ ሳይበላ ተበላ! –ሆዳም! ስለሚበላው እንጂ ስለሚባለው አይጨነቅም!

0
0

aba-mela-esat
ከአዜብ ጌታቸው

አባ መላ ነኝ የሚለው የፓልቶኩ ብርሃኑ ዳምጤ ሰሞኑን የሰራው ስራ ከማንም በላይ የጎዳው እራሱን ነው። ከአንድ ድርጅት ውልቅ ብለው በዚያው ጀንበር ሌላው ድርጅት ጥልቅ የሚሉ፤ ያም ሳይጥማቸው ወይም ሳይመቻቸው ይቀርና ወዲያው ደሞ ወደ ሌላ 3ኛ 4ኛ….. ድርጅት ጥልቅ ውልቅ የሚሉ ጥቂት የማይባሉ ቅብዝብዞችን አውቃለሁ።እነኚህ አይነቶቹ የቻሉትን ያህል እንደ ፌንጣ ዘለው ዘለው በመጨረሻ እዩኝ እዩኝ ያለ ……እንዲሉ፦ ራስን ብቻ አባል በሚያደርገው ዲፕሬሽን ወደ ተሰኘው ድርጅት ይገቡና ፍጻሜያቸውም እዛው ይሆናል።

ሰሞኑን በአባ መላ የታየው ዝላይ ግን በፌንጣ ተምሳሌት ከተገለጹት ቅብዝብዞች የተለየ ነው፡፡ አባ መላ ውልቅ ካለበት የወያኔ ጓዳ ያሞሌ ተመኑን ቀንሶ ዳግም ጥልቅ ብሏል። ስለዚህ ለአባ መላ ተግባር በተምሳሌነት የምትጠቀሰው ፌንጣ ሳትሆን የተፋውን መልሶ የሚውጠው ጉማሬ ይመስለኛል ።

ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድህን ወያኔን ጉማሬ ብለው የገለጹበትም ምክንያት ይህው ነበር፡፤ በነገራችን ላይ ብርሃኑ ዳምጤ በአንድ ቃለ ምልልስ ላይ “አባ መላ” የሚለውን ቅጽል ያወጡለት ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድህን መሆናቸውn (he was my best friend) አይነት ድምጸት) ሲናገር ሰምቸዋለሁ፡፤ የሞተ አይጠይቅ ሆነና ዝም ብለን ሰማነው።

ይሁን እንጂ በበኩሌ እንደሚታየኝ ብርሃኑ ዳምጤ የተሰ|ኘ የተሰፋ ሙዝ የሚሸጥ የምናለሽ ተራ ቁጭ ይበሉ (ምንጭ አብሮ አደጉ)ና የብርቅየውን ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬን ጓደኝነት እንኳን በዕውን በልቦለድ ድርሰትም ቢካተት ለአንባቢ የሚጥም አይመስለኝም፡፤ ልቦለድም ቢሆን እኮ የገሃዱ ዓለም እንጂ የከሃዲው አለም ነጸብራቅ ነው አልተባለም።….

ወደ ቀምነገሩ ልመለስ፦ አዎ ብርሃኑ ዳምጤ እነ ሎሬት ጸጋዬን እየጠቃቀሰ ፕሮፊይሉን ከፍ ከፍ እያደረገ ቢቆይም ሰሞኑን በሰራው ታሪካዊ ክህደት ያበገነው አብሮ አደጉ ያለ ከፈን ምናለሽ ተራ ቀብሮታል።

ለዚህም ነው ብርሃኑ በሰሞኑ ተግባሩ ከማንም በላይ የጎዳው ራሱን ነው ያልኩት፡፤

ከልብ አጢናችሁት ከሆነ የብርሃኑ ዳምጤ ችግር “ሞራል አልባ” መሆኑ ነው። ሞራል አልባ ሰዎች የሌላውንም ሞራል ለመጨፍለቅ ሁለቴ ማሰብ አያስፈልጋቸውም። ሞራል አልባ ሰዎች ፤ ምን ይሉኝ? አይሉም።ምን ይሉኝ የሚለውን ጥያቄ በአግባቡና በቦታው ማንሳት፤ የሞራል ድቀት ከሚያስከትል አደጋ ያድናል። ብርሃኑ ዳምጤን መሰል ሰዎች ይህን ጥያቄ አያውቁትም።

ለዚህም ነው ትናትና እንኳን ለተሰዳቢው ለሰሚው በሚዘገንን ጸያፍ ስድብ ያበሻቀጣቸውን የወያኔ ባለስልጣናት ዛሬ “ማሪኝ ብዬሻለሁ” እያዜመ የሚለማመጠው።

ግን ለምን?

ጥሩ ጥያቄ ነው…ሞራል አልባ ሰው የማንነቱ ነገር ብዙም አያስጨንቀውም። ተደፈረብኝ። ተገሰሰብኝ የሚለው እሱነት የለውም። ስለሚበላው እንጂ ስለሚባለው አይጨነቅም። ለሱ ማንነት? ከሚለው “የስብዕና” ጥያቄ ይልቅ ምቾት፤ ድሎት፤ ቅንጦት፤…..የተመቸ ህይወት ቅድሚያ አላቸው። በአጭሩ ሞራል አልባ ሰዎች ከምንም ከምንም ይልቅ ለሆዳቸው ቅድሚያ ይሰጣሉ።ብርሃኑ ዳምጤም ያደረገው ይህንኑ ነው።

ከወያኔ ኩብለላ

የወያኔ ባለ ስልጣናት የአውራቸውን ሞት ተከትሎ በራሳቸው የውስጥ ችግር ተንጠው፤ ውጭ ለታሰሩት ውሾች ይሰ|ጡ የነበሩትን መደበኛ መሽሩፍ አቋረጡ። በዚህ ምክንያት አለን ከሚሏቸው ተናካሽ ውሾቻቸው አንዱ (አባ መላ) ሰንሰለቱን በጥሶ ወደ ተቃዋሚው ጎራ ተቀላቀለ።

በተቃዋሚው ጎራ ቆይታ፦

ሰንሰለቱን በጥሶ የመጣው አባ መላ አክቲቪስት ተባለና(ይታያችሁ ሞራል አልባ ሰው የሰባዊ መብት ተሟጋች ሲሆን) የድሮ ጌቶቹን አብጠለጠለልን። ሙታንታ ማድረግ የማያውቁ ፍልጦች የሚል ኢ.ሞራላዊ ስድብ አወረደባቸው። እግረ መንገዱንም ሙታንታን ያህል የግል ገበና ሁሉ አውቃለሁ አይነት ራሱን አካበደ።

የጦር ሃይሎች ኤታ ማዦር ሹሙን በዓለማችን የመጨረሻው ደደብ ጀነራል ሲል ተሳለቀበት። የጀኔራሉ ህጻን ልጅ የኦሮሚያውን ፕሬዘዳንት በልምጭ ሲገርፈው “ አባዱላ እንደ ፈርስ ያስካካ እንደነበር ገለጸልን፡፤ ሞራል አልባው አባ ዱላ ለሆዱ ብሎ በህጻን ተገረፈ ብሎ እራት ግብዣ ላይ ያየውን ተረከልን። እረ ማን ቀርቶ… የአዜብን አካላዊ ገጽታ አብጠለጠለ … የበረከትን ሴረኝነት አማሰለ…ስብሃትን በዝሙት በስካርና በገዳይነት ወነጀለ … ብቻ አብዛኞቹ ቱባ ቱባ ባለስልጣናት እጅግ በሚዘገንነው በምናለሽ-ተራ ጩቤ ምላስ ተተለተሉ።ባለ ስልጣናቱ ተዘናግተው ምሱን ባለመስጠታቸው … በሞራል አልባ አንደበቱ ዘመተባቸው። የአዜብ አፍንጫ ጠማማነት ምን የፖለቲካዊ ፋይዳ እንዳለው ባይገባንም ፈገግ ማለታችን አልቀረም።

ብርሃኑ ዳምጤ እንዲህ እንዲህ እያለ በተቃዋሚው ጎራ ቆየ፡፤ ወደ ኢሳት ቢያንዣብብም …. በወያኔ የጎደለበትን ምሱን የሚተካበት ምናምኒት ሊያገኝ የቻለ አልመሰለኝም። ቀጠለና በሳውዲ መንግስት ግፍ የተፈጸመባቸውን ኢትዮጵያዊያንን ለመርዳት በተቋቋመው አለም አቀፍ ግብር ኃይል ገብቶ እድሉን ሞከረ፡፤ እንደ ልኳንዳ ቤት ውሻ አይኑ እየተንከራተተ ምራቁን ገርገጭ አድርጎ ከመዋጥ በስተቀር አሁንም ጠብ የሚል ነገር አልተገኝም። በዚህን ግዜ ብርሃኑ ዳምጤ፤ ከወያኔ ጉያ መውጣቴ ታሪካዊ ስህተት ነው ሲል፡ ታሪካዊ ስህተት ያለውን በታሪካዊ ሞት ሊያርመው ወሰነ።አመቺ ግዜም ጠበቀ።ረዳት ፓይለት ኃይለ መድህንን በቴሬሪስትነት በመፈረጅ ለወያኔ የመጀመሪያውን የምህረት ጥየቃ ደውል ደወለ! ኦሮማይ…….!

ዳግም ወደ ወያኔ…

ብርሃኑ በደርሶ መልሱ ጉዞ ከማንም በላይ የጎዳው እራሱን ነው ያልኩት ያለ ምክንያት አይደለም። በክብር የያዙትን ጌቶቹን አስቀይሞ ሲያበቃ ዛሬ ተመልሶ ለምህረት ደጅ መጥናቱ፤ ዋጋውን ዝቅ አድርጎ ራሱን ለዳግም ሽያጭ ማቅረቡ፤ እንደ ፖለቲከኛ ብቻ ሳይሆን እንደ ሰውም ስብዕናውን ማዝቀጡ እየታየኝ እንጂ ።

ከበድን መሃል ምኑን ይመርጧል አትበሉኝ እንጂ፦ በኔ እይታ ዛሬ ከሰሎሞን ተካልኝና ከቤን የዘቀጠ ሞራል ላይ የሚገኘው ብርሃኑ ነው። ይህን ለመረዳት ደግሞ ከቤን ጋር ያደረጉትን ቃለ መጠይቅ ማድመጥ ብቻ በቂ ነው፡፡ በ

ቃለ መጠይቁ ቤን ሌጌቶቹ ባለው ታማኝነት በመኩራራት የሚሰነዝራቸው አስተያየቶችና ጥያቄዎች “ደግ አላደረክም ቢሆንም እንምርሃለን” አይነት ድምጽ ነበራቸው፡፤ አባ መላም በአንጻሩ ጭራውን እየነሰነሰ ጌታው እግር ሥር እንደሚንከባለል ውሻ አይነት በልምምጥ ስሜት ነበር የሚመልሰው፡፤ ከባሪያም ተራ…..!

ከሞተ ወዳጅ የቆመ ጠላት ይሻላል!

ከብርሃኑ ዳምጤ ድፍረት ሁሉ ያስገረመኝ ፡ ታማኝ በየነንና ማንጓጠጥ መሞከሩ ነው። በርግጥ ወያኔ ከማንምና ከምንም በላይ ታማኝ ቢዋረድላት እንደምትደሰት ሳይታለም የተፈታ ነው፡፤ በዚህ ስሌት ይመስላል ብርሃኑ ዳምጤ ታማኝን ለማብጠልጠል የሞከረው። ነገር ግን አልተሳካም፡፤ ወያኔም ቢሆን ጀግና ታከብራለች ሲሉ ሰምቻለሁና ከብርሃኑ የገለማ ቃል ይልቅ የታማኝን ግልጽ ጠላትነትን የምታከብር ይመስለኛል፡፤ ከሞተ ወዳጅ የቆመ ጠላት ይሻላል ይባል የለ። ብርሃኑ ለኛም ለወያኔም ሞቷል።

ይህን የምለው በታማኝ በየነና በአባ መላ መካከል ያለው ፍጹም የሆነ ልዩነት እየታየኝ ነው፡፤ ቃላቶች ካልተመሙብኝ እስኪ በንጽጽር ልግለጻቸው።

ታማኝ ከአላሙዲን የዶላር ማማ ላይ “እረ ወግድልኝ!” ብሎ ወርዶ ከተገፋው ወገኑ ጎን በመቆም ከፍተኛ የሞራል እርከን ላይ የሚገኝ የህዝብ ልጅ ነው።

ብርሃኑ ደግሞ በአንጻሩ በደም ከጨቀየው ከወያኔ ደጅ የወዳደቀ ምንምን አይቶ፤ ይሁን እስቲ ካወጣነው የሞራል ማማ ላይ ቁልቁል ተምዘግዝጎ የወረደ የግፈኞች ወዶ ገብ ባሪያ ነው።አለቀ።

በነገራችን ላይ ብርሃኑ የወያኔን የምህረት ደወል በቤን አማካኝነት ሲያስደውል፤ አብሮም የኢሳትንና የግንቦት ሰባትን ብዙ ሚስጥር ገጸ በረከት እንደሚያቀርብ ነግሮናል። እውነት እውነት እላችኋለሁ ብርሃኑ እስካሁን ከቀበጣጠራቸው ነገሮች ውጭ አንድም የሚያውቀው ነገር የለም። ለምን በሉኝ? ምክንያቱም ዋናው ቁጭቱ ወደ ሚስጥሩም ወደ …ካዝና ሊያቀርቡት አለመፍቀዳቸው በመሆኑ ነው።ጨዋታ በጋራ ሂሳብ በግል ተባለ….አልወደደውም።

አክቲቪስት ስለመባሉ….

በኢሳት ጋዜጠኞች አክቲቪስት መባሉ ለኔ ብዙም እንደ ጥፋት አልታየኝም። አክቲቪስት የሚለው ስያሜ እንደ ወታደር ቤት በአገልግሎት ዘመን ተመዝኖ የሚሰጥ ሹመት ሳይሆን አመለካከትን ብቻ መሰረት አድርጎ የሚስጥ በመሆኑ ብርሃኑም ወያኔ ማብጠልጠል በጀመረበት ቅጽበት አክቲቪስት መባሉ አልተገቢነቱ አይታየኝም፡፤ በኔ አመለካከት
በእጅጉ የሚያስቆጨኝና ስህተት የምለው “አክቲቪስት” የሚለውን መጠሪያ መስጠቱ ሳይሆን አንድ የ11ኛቢ ተማሪ (ከአብሮ አደጉ የሰማሁት ነው) የምናልሽ ተራ ቁጭ በሉ እነ ሙሉጌታ ሉሌን ከመሰሉ በሳል ሰዎች ጎን ፖለቲካ ሊተነትን መቀመጡ ነው። የሚያናድደኝ ከነታማኝ በየነና አበበ ገላው ሌሎችም ብርቅዬ ኢትዮጵያዊያን እኩል አለም አቀፍ ግብር ኃይል ውስጥ መግባቱ ነው። “እኩያ ቢስ ..!” ይሉ ነበር ቀኛዝማች እንቶኔ እንዲህ አይነቱ ያለአቻ… ….ሲገጥማቸው። ይህ አይነቱ ስህተት እንዳይደገም ሊታሰብበት ይገባል ይመስለኛል።

አሁንም በኔ እይታ ብርሃኑ ዳምጤ (ከሟቹ አለቃው ከጠ/ሚ አጸያፊ አባባል ልዋስና) ከመበስበስ… ወደ.. መታደስ…. እንደገና ወደ መበስበስ ያደረገው የደርሶ መልስ እንቅስቃሴ በአጭሩ ሲቀመጥ፡

እንሆ ብርሃኑ ዳምጤ ጥቅም(ሆዱ) ስለጎደለበት ወያኔን ከድቶ ወደ ተቃዋሚው ጎራ ገባ። የወያኔ ባለስልጣናትን በአጸያፊ ስድብ ማዋረድን ለተቃዋሚው ጎራ እንደ ገጸበረከት አቀረበ።አሁንም በተቃዋሚ ጎራ ለህሊና እንጂ ለሆድ የሚሆን ነገር በማጣቱ የአሞሌ ተመኑን ቀንሶ ራሱን ለቀድሞ ጌታው ዳግም ለሽያጭ አቀረበ። ይህው ነው። መጣ እነሱን ሰደበ …ሄደ..ራሱን ሰደበ!

ብርሃኑ ዳምጤ ከዚህ በኋላስ?

ብርሃኑ ከዚህ በኋላ አይደለም ፖለቲካዊ ህይወት ሰዋዊም ህይወት የሚዋጣለት አይመስለኝም።በቅርቡ አንድ አብሮ አደጉ ብዙ ብዙ አሉታዊ ባህሪያቱን እንዳጋለጠው ሰምተናል። ብርሃኑ የሰሞኑ ተግባሩ ከራሱ ሌላ ማንንም ላለመጉዳቱ ሌላው መገለጫ በይደር ተይዞ የነበረ፤ በቀይ ሽብር ዘመን ከኢህአፓ ውልቅ ደርግ ጥልቅ ብሎ ያስቀጠፋቸውን ሁለት ወጣቶች ጉዳይ ከሟች ቤተሰቦች አንደበት ለማሰማት እንቅስቃሴ መጀመሩ ነው።ይህ ማስፈራሪያ ሳይሆን በቅርብ የማውቀው ወዳጄ እየሰራበት ያለ ጉዳይ ነው።

በኔ እይታ ብርሃኑ የወያኔ ባለስልጣናትን ከሰደባቸው አጸያፊ ስድብ አኳያ እጃቸውን በምህረት የሚዘረጉለት አይመስለኝም። እንደ ሰሎሞን ተካልኝ “የቅንድቡ ውበት” አይነት ሙገሳም የሚያዋጣ አይሆንም። እናም አባ መላ በፓልቶክ ውስጥ ተፈጥሮ በፓልቶክ ውስጥ ኖሮ በፓልቶክ ውስጥ ሞተ ! የሚለውን ዜና የምንሰማበት ግዜ እሩቅ አይሆንም።አባ መላ ሳይበላ ተበላ! ይሏል ይህ ነው…..

ለድህረ ገጾች

ኢሳቶችና ድህረ ገጾች ብርሃኑ የወያኔ ባለስልጣናት በአጸያፊ ስድብ ሲያዋርዳቸው የተቀዳውን ኦዲዮ እየመረጣችሁ በማስደመጥ የምህረት ጥያቄው ተቀባይነት እንዳይገኝ ብታደርጉ እኔን ያየህ ተቀጣ! ነውና አስቡበት….. እያልኩ ከአጼ ቲዎድሮስ ታሪክ ላይ በተዋስኳትና ስሟን ወደ ራሴ በቀየርኳት ስንኝ ልሰናበታችሁ….

ይህንን ሲሰማ ያጓራል ላመሉ
ማናትም ቢላችሁ አዜቧ ናት በሉ!

አዜብ ጌታቸው

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር

አዲስ አበባ “ለእሪታ ቀን”እንድትዘጋጅ ተጠየቀ! “ኢህአዴግ አገር የመምራት ብቃት እንደሌለው አዲስ አበባ ማሳያ ናት!!”

0
0

(ዘ-ሐበሻ 1)በውሃ እጦት፣ 2)በኤሌክትሪክ ሀይል መቆራረጥ፣ 3)በትራንስፖርት ችግር፣ 4)በልማት ሰበብ በሚፈርሱ መኖሪያዎችና የንግድ ሱቆች የተነሳ ዜጎች እየተበደሉ በመሆናቸው፣ 5)በስልክ መስመር ችግር ና በሌሎችም ምክንያቶች የተነሳ ዛሬ የአንድነት ለፍትህና ዲሞክራሲ ፓርቲ የአዲስ አበባ ጽ/ቤት ስራ አስፈጻሚ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በከተማይቱ ደማቅ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግ ይፋ አደረገ። “ኢህአዴግ አገር የመምራት ብቃት እንደሌለው አዲስ አበባ ማሳያ ናት” የሚል ርእስ የተሰጠው መግለጫ ከተማይቱ ከላይ በተጠቀሱት ችግሮች በመዘፈቋ ነዋሪው ከፍተኛ ችግር ውስጥ መውደቁን በመገንዘብ ገዢው ፓርቲ ከተማይቱን ብሎም አገሪቱን የመምራት ብቃት እንደሌለው የችግሮቹ ግዝፈት ዓይነተኛ ማሳያ ነው ብሏል፡፡
UDJ
ሙሉ መግለጫውን ዘሐበሻ እንደሚከተለው እንደወረደ አስተናግዳዋለች።

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)
ኢህአዴግ አገር የመምራት ብቃት እንደሌለው አዲስ አበባ ማሳያ ናት!!

መግለጫ

ሌሎች አገሮች ለዋና ከተሞቻቸው ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የየአገሮቻቸው ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ማሳያ በማድረግ አለም አቀፍ ተቋማትንና ጎብኝዎችን በመጋበዝ የከተሞቻቸውን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ያደርጋሉ፡፡

እንዳለመታደል ሆኖ ግን በብዙዎች የአፍሪካ አገራት የአህጉሪቱ መዲና ተደርጋ የምትጠቀሰው አዲስ አበበባችን ከጊዜ ወደ ጊዜ ወደ ኋላ አየተጎተተች ለኑሮ ምቹ ከሆኑ ከተሞች ምድብ መቀላቀለ ተስኗት ለነዋሪዎቿ የማትመች የፈተና ምድር ሆናለች፡፡
UDJ 2
ኢህአዴግ ራሱን ልማታዊ መንግሥት በማድረግ ከሰየመበት ቅጽበት አንስቶ በልማት ሰበብ ዜጎች ከመኖሪያቸውና ቤተሰቦቻቸውን ከሚያስተዳድሩበት የንግድ ቦታ እንዲፈናቀሉ ተደርገዋል፡፡ በከተማይቱ እንዲነሱ የተደረጉት የንግድ ሱቆች በአብዛኛው በኪራይ ቤቶችና በቀበሌ ስም የተመዘገቡ በመሆናቸውም በሱቆቹ በመነገድ ይተዳደሩ የነበሩ ቤተሰቦች ባዶ አጃቸውን እንዲቀሩ ተደርገዋል፡፡

በአዲስ አበባ እየተካሄደ ያለውን የመንገድ ዝርጋታ የተነሳ የተጠና ሥራ ባለመሰራቱ ከፍተኛ የህዝብ ገንዘብ የወጣባቸው መንገዶች ለምረቃ በበቁ በጥቂት ቀናት ልዩነት እንዲፈርሱ ተደርገዋል፡፡ የከተማው ነዋሪ ለሚጠቀምባቸው የመጓጓዣ አውታሮች ተለዋጭ መንገድ ባመዘጋጀቱም ለተጨማሪ ወጪ ተዳርጓል፡፡ ትራንስፖርት ማግኘት በሁሉም አካባቢዎች አስቸጋሪ በመሆኑ የከተማይቱ የሥራ እንቃስቃሴ ተዳክሟል፡፡ መንግሥት ‹‹የምትታለብ ላም›› በማለት የሚጠራው የኢትዮ ቴሌ ኮም አገልግሎት የለም የሚባልበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ጭምር በኢትዮጵ ቴሌኮም የተንቀራፈፈ አገልግሎተ የተነሳ ባንኮችና የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ለደምበኞቻቸው ተገቢውን ግልጋሎተ ማበርከት አልቻሉም፡፡

የታክሲ ወረፋ በአዲስ አበባ

የታክሲ ወረፋ በአዲስ አበባ


የከተማይቱ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር የተወሰኑ ሠራተኞች ችግር እንደሆነ ተጠቁሞ ሠራተኞች ለስንብት ቢዳረጉም የኤሌክትሪክ መቆራረጥና ለረጅም ግዜ መጥፋት የከተማይቱ ኢንዱስትሪዎች ፤ንግድ ተቋማትንና ነዋሪውን እያማረረና ህይወቱን እያመሰቃቀለ ከመሄድ ውጭ ምንም አይነት ለውጥ አልታየበትም፡፡ በከተማይቱ ውሃ ማግኘት እንደ ትልቅ እድል መቆጠር ጀምሯል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ የከተማይቱ 75% ነዋሪ ውሃ እንደሚያገኝ ቢናገሩም መሬት ላይ ያለው እውነታ ግን በተቃራኒው ሆኗል፡፡ ጊዜያቸውን በትምሀርት ገበታቸው ላይ በመገኘት ማሳለፍ ይገባቸው የነበሩ ተማሪዎች ውሃ ለመቅዳት ረዥም መንገድ ለመጓዝ በመገደዳቸው የትምህርት ጊዜአቸው እየተበደለ ይገኛል፡፡

በአጠቃላይ ከተማይቱን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ የከተማይቱ ነዋሪ ለሚገፋው አስቸጋሪ ህይወት ተጠያቂ ነው፡፡ ድርጅቱ አገሪቱን የመምራት ብቃት እንደሌለውም የወቅቱ የአዲስ አበባ ሁኔታ አይነተኛ ማሳያ ነው፡፡

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የከተማይቱ ነዋሪ እየገፋው የሚገኘውን ፈታኝ ህይወት በማጥናት ህዝቡን በተለይም የከተማውን እና የዙሪያ አካባቢዋን ነዋሪ በማደራጀት በቅርቡ ‹‹የእሪታ ቀን›› በማለት ሰይሞ በ1ወር ጊዜ ውስጥ ሠላማዊ ሠልፍ ለማድረግ የወሰንን መሆኑን እየገለፅን የአዲስ አበባና አካባቢዋ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፉ በሚደረግበት ቀን በነቂስ በመውጣት በስርዓቱ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ለመግለፅ እንዲዘጋጁ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ድል የህዝብ ነው
መጋቢት 11 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም
አዲስ አበባ

ቤተክርስቲያን መምህር ግርማን ፎርጂድ ደብዳቤ በማሰራጨት ወነጀለች

0
0

Memeher Girma
(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን “መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ” በሚል ስያሜ የተበተነው ደብዳቤ ሕገ ወጥ በመሆኑ የሚመለከተው ሁሉ ይህን ግንዛቤ እንዲወስድ አሳሰበች፡፡ “መምህር ግርማ ወንድሙ ከፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በመላው ዓለም እየተዘዋወሩ እንዲያገለግሉ ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል” በሚል መምህር ግርማ እያሰራጩት ያለው ደብዳቤ ከቤተክርስቲያኒቱ ጽህፈት ቤት ተፈርሞ ያልወጣ የማጭበርበር ደብዳቤ ነው ሲል በአባ ገርማ (ሊቀጳጳስ/ዶ/ር) የብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርል ልዩ ጽህፈት ቤት የውጭ ግኙነት ሃላፊ ስም መጋቢት 10 ቀን 2006 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ተገልጿል።

ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም መምህር ግርማ የበተኑትንና በመላው ዓለም ከፓትርያርኩ ተዘዋውሬ ሃብተ ፈውስን እንድሰጥ ተፈቅዶልኛል የሚለውን ደብዳቤ ማስተናገዷ የሚያወስ ሲሆን አሁን ደግሞ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ የፓትሪያርኩ ልዩ ጽህፈት ቤት የወጣውን ደብዳቤ በማስተናገድ ፍርዱን ለአንባቢ ትተዋለች።

ቀጥሎም ፎርጂዱን ደብዳቤ እንዳትቀበሉት ሲል የወጣውን እና መምህር ግርማ ያሰራጩት የተባለውን ደብዳቤ በተከታታይ ለግንዛቤ አቅርበናቸዋል።

ዘ-ሐበሻ መምህር ግርማን በዚህ ህገወጥ የሆነ ደብዳቤ አሰራጭተዋል በሚል በቀረበባቸው ውንጅላ ዙሪያ ለማነጋገር ያደረገችው ሙከራ ባይሳካም እንዳገኘናቸው ሃሳባቸውን ለማቅረብ እንሞክራለን። ሆኖም ግን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች መምህር ግርማ ነሐሴ 25/2005 ዓ.ም ደብዳቤ ተጽፎልኛል ብለው ደብዳቤውን ከበተኑት ከ7 ወር በኋላ ቤተክርስቲያን ጉዳዩን ማስተባበሏ ከበስተጀርባው አንድ ጉዳይ ሊኖር እንደሚችል ይናገራሉ።

የመምህር ግርማ ደብዳቤ ፎርጂድ ነው አትቀበሉት ሲል የተጻፈው ደብዳቤ
memeher girma holy sionod

መምህር ግርማ በአቡነ ማቲያስ ሃብተ ፈውስን እንድሰጥ ተፈቅዶልኝ ደብዳቤ ተጽፎልኛል ሲሉ የበተኑት ደብዳቤ፦

Memher Girma

Memher Girma

ለአልሙዲ “ማፅናኛ”

0
0

(ከጋዜጠኛ ተስፋዬ ተሰማ)

alamudi 1
በቅርቡ ባህርዳር ላይ በተካሄደው የኢትዮጵያ ስፖርት በአል ሼኽ አልሙዲ በክብር እንግድነት ተጋብዘው ነበር። የበአሉን መክፈቻ በቲቪ ስከታተል አንድ ጥያቄ ወደ በአእምሮዬ መጣ። አልሙዲንን የክብር እንግዳ አድርጐ መጋበዙ ለምን አስፈለገ?..ብዙ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ። “የገዢው ፓርቲና የባለስልጣናቱ ታማኝ ወዳጅ ስለሆኑ፣ በባህርዳሩ ስታዲየም ግንባታ ድርጅታቸው ስለተሳተፈ ወይም ሼኹ ለስፖርት ያላቸውን ፍቅር በማየት..” የሚሉ ነገሮችን መደርደር ይቻላል።
በእኔ ግምት አልሙዲ በባህርዳሩ በአል በእንግድነት የተጋበዙት በሰሜን አሜሪካ ስፖርት በአል ላይ ስለተዋረዱ የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት የፈጠርዋት ማፅናኛ ትመስለኛለች። ባለፈው አመት እዚህ ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በአንድ ሳምንት ሁለት የኢትዮጵያ ስፖርት በአል ተከበሮዋል። አንድኛው በሼኽ አልሙዲና የዳይስፖራውን ማንነትና ፍላጐት ባልተገነዘቡ ወዳጆቻቸው የተዘጋጀ ነበር። በነዚህ ወገኖች ግምት “ዳያስፖራው በተወሰኑ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት ካድሬዎች የሚሽከረከር የዋህ ህዝብ” አድርገው ይወስዱታል።
አሜሪካ ሀገር ከኅይለስላሴ ጀምሮ በደርግ ጊዜ ከዛም በኋላ የመጣው አብዛኛው ኢትዮጵያዊ (በምንም መንገድ አሜሪካ ይምጣ) ለዘሩ፣ ለጐሳው ሳይሆን ለኢትዮጵያዊነቱ ጥልቅ የሆነ ፍቅርና ክብር አለው። በዚህ ምክንያት የኢህአዴግን የዘር ፖለቲካ አይደግፍም። ከደጋፊዎቹም ጋር የማይታረቅ ቅራኔ ውስጥ የገባው በዚህ አገር ወዳድ አቋሙ ነው። ይህ እውነት ያለገባቸው አልሙዲና ተከታዮቻቸው በስፖርቱ አስታከው ዳያስፖራውን እንቆጣጠራለን በማለት በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ቢከሰክሱም አልተሳካላቸውም። ባዶ ስታዲየም ታቅፈው ነው የቀሩት። ሁለተኛው ኢ.ኤስ.ኤፍ.ኤን የሚባለው ኢትዮጵያዊ ፌዴሬሽን የነሱን ያክል ገንዘብ ሳይኖረው በርካታ ህዝብ ከጎኖ ማሰለፍ ችሎዋል። እንዲያውም ስታዲየሙ ሞልቶ ሰው እስኪመለስ ድረስ። በዚህ በአል ከፍተኛ የሆነ የአንድነትና የአገር ፍቅር ስሜት የታየበት፣ የኢትዮጵያ ባንዲራ ከፍ ብሎ በብዛት የተውለበለበበትና ያሸበረቀበት፣ ሰዎች ከብሄራቸው ይልቅ ኢትዮጵያዊነታቸውን ያገነኑበት ትልቅ በአል ነበር።
ባዶ ስታድየም የታቀፉትና አፍረው በውርደት ለተመለሱት አልሙዲ የባህርዳሩ እድል በማፅናኛነት ተሰጣቸው። ኢትዮጵያዊያን በነፃነት በሚኖሩበት አሜሪካ ግን አልሙዲ በገንዘባቸው የህዝብን ድጋፍ መግዛት አይችሉም። በገንዘብ ምንም ማድረግ እንደማይችሉም ሊያውቁት ይገባል።

አፍንጫህን ላስ –አቶ ሂደት።

0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ ሲዊዘርላንድ ዙሪክ
New Picture (19)
እኔ ነኝ አቶ ሂደትን አፍንጫውን እንዲልስ የፈለኩት። ሃሳቤን የሚጋራ ትብብር ካለም ደስታውን አልችለውም። በ16.03.2014 ጀንበር ዘቅዘቅ ከመለቷ በፊት ዘሀበሻ ስገባ አንድ አዲስ መረጃ አገኘሁ። የአንድነትና የመኢአድ ቅድም ውህደት መሰናዶ።
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/13623 ዘግዬት ብሎ ደግሞ ማምሻ ላይ ለሁለተኛው ቀን በደብተራ ክፍል አዲሱን ዜና አበሰሩ ለታዳሚው የአንድነቱ አቶ ሃብታሙ አያሌው። እንደ ድሮው ቢሆን እንዴት? ወዴት? ለምን? እያልኩ መንፈሴን አመሰው፤ አውከው ነበር። አሁን ግን አዳማጠኩ አቶ ሂደትን ማዬት ነው ፍሬውን። በቃ! ጅልነት ቀረ ወላለቀም። ነገም የሰይጣን ጆሮ ይደፈንና ከባዶ ሳጥን ቆጠራ በኋላ አቶ ሂደት ሌላ ትዕይነት ይዞ ከች ቢል አፍንጫህን ላስ በመጣህበት መንገድ ብዬ ቅንጡን አብርሬ ማሳፈር። ሞኙን ይፈልግ …. ይበቃል የተዳቀቅነው —-

ይልቅ አቶ ሀብታሙ በ16.03.2014 በነገሩን ሰበር ዜና ላይ የተፈለፈለ ቁምነገር አብሬ አዳመጥኩኝ። ኮረቻ ላይ ቁጢጥ ያለ „ኢጎ“ አላሰራም ካላ በመጣበት መንገድ ለመሸኘት መወሰኑን። ይህ ማለፊያ ነገር ነው። ግን ላይ ብቻ ነው „ኢጎ“ ያለውን አቶ ሀብታሙ? ታችም አለና ታቹም ላዩም በተገባው ይቃኝ ባይም ነኝ። እንዲውም መጋኛው ያለው ከታች ይመስለኛል። ለማንኛውም እኔ ጅልነትን ስለቀበርኩት አቶ ሂደት በፈለገው ቅርጽና ይዘት ሊያወናብድ ቢያነፈንፍ ቅስሙን እንኩት። የጀመረውን የማተራመስ ማሳ ለቀቅም አድርጌለት ከቻልኩ ማገዝ በሰተቀር ግን መፈሳፈስ፤ መፈራረጅን፤ አጋ ለይቶ በገጀሞ መከታከትን እሱ እንደሚጠብቀው ስለማውቅ አፍንጫህን ላስ ብዬዋለሁ። አሁን ተዋውቀናል። በዛች ቆልማማ አፍንጫው እሱ ከመሳቁ – ከመሳለቁ በፊት እኔ ቅድም …. ማን ሞኝ አለ።

ሌላው አቶ ሂደትን የምጠብቀው ቁም ነገር እንዳለ እስቲ ላስታውስህ። በዚህ ገጥመህ በሰፋኽው ማሳህ ብቃት ያላቸው ሴቶች ከገንዘብ ያዥነት ወይንም አቻዎቻቸውን ከሚመሩበት „የሴቶች ጉዳይ ክፍል“ ሸገር ያለ ወንዝ የሚያሻግር ላቅ ያለ ድርሻ እንዲያው ታምነው ይስጣቸው ይሆን?! ያው በአጭሩ ቢቀረጠፍም አንድነት የመጀመሪያው ፓርቲ ነው ክብርት ዳኛ ብርቱካን ሜዴቅሳን የሊቀመንበርነቱን ቦታ ሲሰጥ። ለዚህም ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ከአንድ ብሄራዊ ፓርቲ መሪዎች ዝርዝር ታሪክ ውስጥ አይኔ በክብር አለችና።
ከዛም በኋላ ምን ነበረ? ርዕዮትዬን ስጠብቅ ጭራሽ ተፈናቃይ አደረጋት አቶ ሂደት። አሁንስ ከቶ ምን እዬተመከረ ይሆን? …. እርግጥ እነ ወይንዬም ጠንከር ብለው ጎልተው እዬወጡ ነው። …. „በሴትነታችን ሳይሆን በብቃታችን“ በማለት …. ለማንኛውም ዘመነኛው ሂደት ይጠበቃል። መፍትሄውን እዬዘለለ ይህ ሂደት የሚባል ጉድ እኛንም አሞ ከሞ ያጫውተናል እንጂ የድሉ መናገሻ ፍሬ ነገር እኮ ይታወቃል። እነ ሚሚ እነ ቱቱ እነ እሙዬ እነ ሜላት ተናገሩ እኮ! ውይ! አንድ ነገር ረስቼ „ነገረ ሴቶችን“ የሚያዳምጥ ጆሮ የሚገዛበት ቦታ የምታውቁ አላችሁን? ከሰማችሁ እባካችሁ ….?! ለሚነግረኝ ትንሽ ሽልንግ ቢጤ በመቀነቴ ቆጣጥሬ እዬጠበኩ ነው ….

ሌላ ምን ነበር? ብቃትና አቅም አዬሁኝ ከ15.03.2014 ከአቶ ሃብታሙ አያሌው የደብተራ ሩም ቆይታ። ወያኔ አዘጋጅቶ በነበረው የሚዲያ ፓናል ዲስክሽንም ክርክም ያለች፤ ክሽን ያለች አንጀት አርስ ቦንብ ነበር ያጎረሱት ሽፋታውን ወያኔ፤ ወያኔ ከጫካ ወደ ከተማ ኑሮውን ሲያደላድል የ2ኛ ክፍል ተማሪ የነበሩት አቶ ሃብታሙ አያሌው። ለነገሩ አዲስ አበባም እኮ ለወያኔ ጫካው፤ መንፈሱ ጫካ፤ ህሊናው ጫካ …. ለአራዊትነት የተፈቀደ ግዛት ….. በጫካ ቲወሪ መደናበር —-

የአንድነት አዲስ መዋቅር፤ የመድረክ ምስረታ ሰሞናትም የአደራ ጠባቂው አቶ አንዶአለም አራጌ እንዲህ ከዓይን ያውጣህ የተባለ መንፈሰ ሊጋባ ነበር። የእኔ ስጋቴ እንዲህ ጎልብቶ የወጣ አቅምን ማዬት የሚፈልጉ፤ ማድመጥ የሚሹ፣ እንደ ብርቅ የሚያዩ፣ ይህን ሃብት ጥቅም ላይ ለማዬት የሚጓጉ የመኖራቸውን ያህል ተመሳስለው ያሉ የግል ኢጎ ቁስለኞች ደግሞ ከአረሙ ጋር በማበር ሌላ የጨለመ ትዕይነት እንዳይመጣ እንቅልፍ አለባው ሥርጉተ ትሰጋለች። ይፈቀዳል አይደል መስጋት …. ? ? ?

እኔ እነዚህ የትውልድ አዲስ ተረካቢ ወጣቶቹ ጥንካሬ ፈጽሞ የማይጠበቅ እዬሆነበኝ ነው። ግንዛቤያቸው፣ ዕያታቸው ከምኑ ነው የዛቁት? ይገርማል – ይገራል። ከመራራው የዕንባ ጅረት ሳይሆን አንደማይቀር ሰማይ ቤት ላይ ያለው የክሮስፖንዳንስ ሠረተኛ ጠቁሞኝ ነበር አንድ ቀን እንደ ዋዛ። …. ታዲያ እኛ ይህን የሚያሰተናግድ ንጡህ መንፈስ አለን ነው ጥያቄው … ከዚህው ከአቶ ሃብታሙ ማህደር ሳልወጣ ትንሽ ቆዬት ባለቸው የቃሌ ክፍል ቃለ ምልልሳቸው „መንገዱ ተጀመረ“ ልጃቸውን የትዳር ጥንዶቹ በጉራጌኛ የጠሩበት ስያሜ ነው። የኢትዮጵያን ቀለማም ማንነት እንዲህ ፈቅደው ያስጌጡ ናቸውና ተዚህ ላይ አቶ ሂደትን ቸር ወሬ ስላሰማኝ ለጥ ብዬ አመሰገንኩት። ውሳኔው ያስተምራል – ይመራል። የአዲሱን ትውልድ መንፈስም አሳምሮ ያሳያል …. ሌሎቻችንም ይልመድብን። እኔ ትርጉም የሚሰጡኝን ነገሮች በአግባቡ ነው አክብሬ የምይዛቸው። ጠብ ብላ የምትፈስ ጠበል የለችም። ሥጋና ምን ተባለዬ ቤት አይደለሁም ….

ገጥሞ መስፋት ያልኩት በአሉታዊ እንዳይታይብኝ። አዎንታዊ ነው። አኔ እራሴ ተገጥሜ ተሰፍቼ ነው በህይወት ቁሜ እንደ ጥንቱ ከሞት ተርፌ ሰው ሆኜ ቆሜ ያለሁት። የእውነት እምተርፍበት ሁኔታ በጣም ስስ ነበር። ግን ፈጣሪ ይመስገን ተገጥሜ ከተሰፋሁ በኋላ ሶስት ዓመት ተጨመረልኝ። በኋላም ይመጣሉ ተብለው የተሰጉት ነገሮችም በሃኪሞቼ እንደተተነበዩት አይደለም በጣም በእጅጉ የቀነሰ ነው።

ሌላ አንድ ነገር የቀረ ደግሞ አለኝ። አቶ ሂደት አለህ? ሆሆ ትሰማኛለህ? ከልብህ እባክህ አዳምጠኝ – ቢተ? (bitte? እባክህ?)? ገጥመህ ስትሰፋ ደስ ብሎህ ፍንክንክ ፍልቅልቅ ብለህ ተቀበሉኝ እንደምትለን ሁሉ „ተገጥሜ ለመሰፋት ጊዜዬ ገና ነው“ ላላው ልጅህ ደግሞ ነፃነቱን ፈቃዱን ጠብቅለት። ከነፃነቱ ጋር እዬሄድክ አትላተም። „ጊዜ ገቢረ ለእግዚአብሄር“ ይላል ወንጌሉ። እሱን መለስ በልና ገልበጥ አድርገህ ከቃሉ ጋር ጥድፊያህን አሰማማው። „ሲሮጡ የላኩህም“ አትሁን። አደብ የትውልዱ መንፈስ ነው፤ ለነገሩ ይሄ ሚስጥር ጠጠር ብሎብሃል አይደል?። ከሌለህ ደግሞ ቅዱስ ወንጌል ያለውን ይሄው እኔው እህትህ አስታወስኩህ። ካለጊዜው የተፈጸመ ድርጊት ታምራዊ አንድ ነገር ብቻ ነበር። የቃና ዘገሊላ የድንግል ማርያምና የልጇ ፍቅራዊ ሂደት። „መጠበቀን“ የመሰለ ነገር የለም። መጠበቅ ለእኔ የዲያመንድ ጮራ ነው።

ለነገሩ አንተ መስማማትን አትወድም። በምን አቅልህ? እንደ ሽፍታው ወያኔ እኮ አቅልህ የተዘቀዘቀ ሸውሻዋ ነህ። ደግሞ ታስፈራራለህ ወዮ! እያልክ አትስማሙ እያልክ፤ በእንትን በቅብጥርስ እያልክ ስታምሰን ከረምክ። አሁን ተነቃብህ። አፍንጫህን ላስ ተበላክ …. ጉድህ ፈላ …..። እዬተወላገዱ ሙድ ማሳት ተመነጠረ። አዬህ አቶ ሂደት …. መንፈስ ሲሰበሰብ አቅም ወግ ይደርሰዋል።

ብቻ አደራ እንደዚህ ለግለግ እያሉ የሚወጡትን ቀንበጦቼን ወደ ቃሊቲ …. እንዳታስባቸው እንጂ፣ እኛም ልክ እንደ ጀግናው አበበ ቢቂላ ቀደመንህ ልብ ገዛን። ከአንተ ጋር አብረን ወገኖቻችን በሰባራ ሰንጣራው መውቃት፤ መድቃት፤ ማብጠልጠል ቅርት፤ ምን ይውጥህ? ትላንትን አሳዬህን፤ ዛሬንም ሻምላ ጋሬጣ አዘጋጅተህ በሉ ልያችሁ የማን ደም ፈሰሰ ቀረ። „አሞራው በረረ ቅሉ ተሰበረ“ ሆነልህ – ትልምህ። እኛ ምናችን ሞኝ?! እቴ! ሞኝህን ፈልግ ብለን … በተደሞ ማዬትን መረጥን። ስንችል ደግሞ የምንችለውን ማጉረስ። ምን ይውጥህ?! ….. አንተ ምንትሶ – ቅብጥርሶ፤ ደልቅ ከዘመንኛው ጥጋበኛ ወያኔ ጋር … አንድ ቀን አንተም እንዲህ እዩዩኝ ስትል እንክት ትልና …. እንደ ጦር የምትፈራው „ገናናው ኢትዮጵያዊነት“ በአኃቲ ማዕዶት … በሽንጣም ሞሰብ ቅብጥን ቅልጥ በማለት በናፍቆት ማር የምታዘንበው ሀገራችን ላይ … ተግባባን ጌታው አቶ ሂደት። ለነገሩ ሰንደቅአላማን ገንባሌ አድርጎ ቀን ሳይታደል ካለአለአቅሙ፣ ካለወርዱም የተኮፈሰው ውሽልሽል የጎጥ ቅራቅንቦ „ኢትዮጵያዊነት“ ከእኔ ወዲያ ላሳር እያለ ነው አሉ …. አያልቅበት ቀዳዳ ዲሪቶ መጣፍ። ሰው ይተዘበኛል አይል? አይኑን በጥሬጨው ያሸ ጉድ …. „መሳቂያው ፓርላማ“ አለ አቤ ቶኪቻው። በል ከመሰናበቴ በፊት ተጠይቅ አስሰኪ አንድ ጥያቄ ከቶ መቼ ነው ከዚህ ኪስ አውላቂ የድቡሽት ቤት ጎጠኛ ሽፍታ ጋር የምትፋታው? የናፈቀኝ አሱ ነው …. ህልም አይከለከል ነገር ..

የእኔዎቹ እንዴት ናችሁልኝ። አብረን በመቆዬታችን ደስ ሲለኝ ስንበቱን ሳስብ ደግሞ ክፍት አለኝ። ባር ባር እያለኝ ናፍቆቴን በፍቅር ጥበብ አሳምሬ ቸር እንድተሰነብቱልኝ ተመኝቼ ልሰናበት። መልካም ጊዜ። ማይክ ፍሪ ….

እልፍ ነንና እልፍነታችን በተግባር እልፍ እናድርገው።

እግዚአበሄር ይስጥልኝ።

ሥርጉተ ሥላሴ።

“ሰው በላ” በሆኑት የኢህአዴግ ሙሰኞች ላይ ኮሚሽኑ ለምን ይሽኮረመማል?

0
0

ሳሙኤል ተወልደ በርሔ/ሃርስታድ ኖርዌይ/
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ በነበሩበት የጠቅላይነት ዘመን የተጀመረው እና ቀጣይነት እንደሚኖረው የተነገረለት የከፍተኛ ባለስልጣናት ‹‹የሀብት ምዝገባ››ን የበላው ጅብ ምነው አልጮህ አለ?…ጥያቄው ይህ ነው፡፡ የሚመለከተውም ጸረ ሙስና ኮሚሽንን ነው፡፡ ጸረ ሙስና ኮሚሽን የገቢዎች ባለስልጣናቱን እነ አቶ መላኩ ፈንቴን በሙስና ወንጀል ጠርጥሮ ካሳሰራቸው በኋላ ፀረ ሙስና ስሙ የመታደስ አዝማሚያ ታይቶበት ነበር፡፡ ትናንሽ ባለስልጣናት ላይ እንደሚበረታ የሚነገርለት ፀረ ሙስና ኮሚሽን የነ አቶ መላኩ ፈንቴን በቁጥጥር ስር መዋል ተከትሎ ከአይን ያውጣህ ተብሎ ነበር፡፡

ይህ ራሱን የቻለ ጉዳይ ቢሆንም፣ ለዚህ መጣጥፍ መነሻ የሆነኝ ግን ተጀምሮ የተቋረጠው ወይም ወደፊት ይፋ ይሆናል ተብሎ በእንጥልጥል የቀረው የከፍተኛ ባለስልጣናት የሐብት ምዝገባ ይፋ የማድረግ ሒደት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ሙስና እና ሙሰኞች እንዳሉ ባለጉዳዩ ኢህዴግም ያምናል፤ ያውቃል፡፡ የሀገር እና የህዝብን ሀብት የተለያየ ቅርንጫፍ ካለው የሙስና ግንድ መታደግ የሚቻለው ባለስልጣናትን በማሰር ብቻ አይመስለኝም፡፡
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ባለቤት ወይዘሮ አዜብ መስፍን በአንድ ወቅት፡- “መለስ የ6 ሺ ህብር ደመወዝተኛ ነበር፡፡ ቤተሰቡን ከወር እስከወር ያስተዳድር የነበረውም መንግስት በሚከፍለው ደመወዝ ብቻ ነበር…” በማለት እንደተናገሩ (እንደተሳለቁ) አይዘነጋም፡፡ ለተቀረው ኢትዮጵያዊ ቀርቶ ለራሱ ለኢህአዴግ አባላት እንኳን ፌዝ የሆነው የወ/ሮ አዜብ መስፍን ንግግር በፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዘንድ እንዴት እንደሚታይ (እንደሚተረጎም) አላውቅም፡፡ ኮሚሽኑ “በ6 ሺህ ብር ደመወዝ ነበር የምንተዳደረው” ከሚለው የወይዘሮዋ ንግግር ተቃራኒ የሆነ የሀብት ክምችትን ያጋልጥ ይሆን?…ወይስ ወይዘሮ አዜብ እንዳሉት “የመለስ ቤተሰብ በ6 ሺህ ብር ይተዳደር ነበር፡፡ አሁንም ቢሆን ከሚቆረጥላቸው የባለቤታቸው የጡረታ ገንዘብ ውጪ ቤሳቤስቲን የላቸውም” በማለት ፖለቲካዊ ጥብቅና ይቆምላቸው ይሆን?…አብረን የምናየው ይሆናል፡፡
“ዓላማዬ ሙስናን እና ሙሰኞችን ማጋለጥ ነው፡፡ ህብረተሰቡም ይተባበረኝ…” እያለ በተደጋጋሚ የሚደሰኩረው ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለረዥም ጊዜ አፍኖ ያቆየውን (“ሲመዘግብ የነበረውን”) የባለስልጣናት ሀብት ያለ አንዳች “ሴንሰር” ወይም ኦርጂናሉን ንብረታቸውን ይፋ እንደሚያደርግ ሰሞኑን በድረ-ገፆች ከተሰራጩ መረጃዎች መገንዘብ ይቻላል፡፡ እዚህች ጋር ጥያቄ አለኝ፤ ኮሚሽኑ “ይፋ” የሚያደርገው የባለስልጣናት ሃብት በምን ዓይነት የምርመራ ስትራቴጂ የደረሰበት ነው?…ወይስ ባለስልጣናቱ “እኔ የመንግስት ሰራተኛ ነኝ፤ ከዬት አምጥቼ ሀብት አከማቻለሁ?…ያለችኝ ይቺ ናት” ብለው የተናዘዙትን ጥቃቅንና አነስተና ንብረት ነው “ይፋ” የሚያደርገው?
“ያለቺኝ ይቺ ናት፤ ይህችኑ መዝግብ” ተብሎ የተሰጠውን ሀብት ይፋ የሚያደርግ ከሆነ በህዝብ ንብረት ላይ መሳለቅ ነው የሚሆነው፡፡ የተለያዩ ዓለም ዓቀፍ ተቋማት በቢሊዮን የሚቆጠር በሕገ-ወጥ መንገድ ገንዘብ ከኢትዮጵያ ወደ ውጪ እንደሚኮበልል በየጊዜው ያጋልጣሉ፡፡ እንዲህ ያለ ዘግናኝ ገንዘብ መቼም በተራ ኢትዮጵያዊ ወደ ውጪ ይኮበልላል ማለት የዋህነት ነው፡፡ በኮበለለው እና ወደፊትም በሚኮበልለው የህዝብ (የሀገር) ገንዘብ ውስጥ የቱባ ባስልጣናት እጅ እንዳለበት አያጠራጥርም፡፡ ታዲያ ኮሚሽኑ በምን መንገድ ነው በከባድ ሙስና ኮብልሎ በውጪ ሀገር ባንኮች የተከማቸውን ገንዘብ የሚያጋልጠው?…የሚለው ጥያቄ የግድ አጥጋቢ ምላሽ ማግኘት አለበት፡፡
ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የነ አባዱላ ገመዳን፣ የነበረከት ስምኦንን፣ የነዶ/ር ደብረፅዮንን…ትክክለኛ ሀብትና ንብረት ካላሳወቀን ኮሚሽንነቱ ቀርቶ እንደ መርካቶ “ቁጭ በሉ” እያታለለን ቢኖር “መልካም” ነው፡፡ ምክንያቱም፡- የመርካቶ “ቁጭ በሉ” ለተነሳለት “ዓላማ” ባዳ በመሆኑ የትኛውም ዓይነት ኃላፊነት ደንታ አይሰጠውም፡፡ ስለሆነም በኮሚሽነር አሊ ሱሌይማን የሚመራው ፀረ-ሙሽና ኮሚሽን የበረከት፣ የደብረፂዮን ወይም የአዜብ “ዓይን ገረፈኝ” ብሎ የተዛባ መረጃ የሚያቀርብልን ከሆነ “ውጉዝ ከመ አርዮስ” ከመባል አይድንም፡፡
ምክንያቱም ከዚህ ምስኪን ሕዝብ የተሰበሰበ ገንዘብ እንደ “ቦዘኔ” ልጅ የትም ወጥቶ ሲቀር ከማየት በላይ የሚያስቆጭም የሚያናድድም ድርጊት የለም፡፡
ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ከደብረፂዮን ጋር ሲሆን ሕወሓትን፣ ከበረከት ጋር ሲሆን ብአዴንን፣ ከአባዱላ ጋር ሲሆን ኦህዴድን…መምሰሉን ትቶ ለኢትዮጵያ ህዝብ ዘብ እንዲቆም ከዛሬ ጀምሮ በአስቸኳይ ዝግጁ መሆን አለበት፡፡ ካለበለዚያ ካገኘው ወይም የሩሲያ ቮድካ ከጋበዘው ባለስልጣን ጋር ሁሉ እንደ እስስት እየተመሳሰለ የኢትዮጵያን ህዝብ ላብ እንደ ደም መምጠጥ እንደሌለበት ካሁኑ መገንዘብ አለበት፡፡ እንዲሁም እንደ ልጃገረድ መሽኮርመሙን አቁሞ የባለስልጣናቱን ሀብት “ይፋ” ማድረግ አለበት፡፡ ምክንያቱም ሙስና የገንዘብ ዝርፊያ ቢሆንም፤ እንደ “ሰው በላ” አውሬ ሀገሪቱን ቀርጥፎ ይጨርሳታል ባይ ነኝ፡፡
ከፍተኛ ባለስልጣናቱ ያላቸውን ሀብት በይፋ ካስመዘገቡ እና የተመዘገበው ሀብታቸው ለህዝብ ይፋ ከሆነ፣ ከደሞዛቸው በላይ የሆነ መኪና ለመንዳት ብዙም ድፍረት እንደማያገኙ ይታመናል፤ ምናልባት ዓይን በጨው በማጠብ የመጣው ይምጣ ብለው ካልፎከሩ በስተቀር፡፡ እናም ፀረ ሙስና ኮሚሽን ሆይ ያኔ ማለትም የዛሬ ሁለት እና ሶስት ዓመት ገደማ የከፍተኛ ባለስልጣናት ሀብትን መዝግበህ አንደነበር አይዘነጋም፡፡
ወይስ የከፍተኛ ባለስልጣናቱ ፊት እንደ እሳት ገረፈህና የነሱን የሀብት መጠን ለማሳወቅ ጉልበትህ ከዳህ? በርግጥ ልክ ነህ፤ የቱባ ባለስልጣናቱን ሀብት መዝግበህ ይፋ ከምታደርገው የሀብት መጠን በላይ ህንፃ ሲገነባና መኪና ሲሸጥ ያገኘኸውን አይነኬ ባለስልጣን መንካት ምን ያህል ከባድ እንደሆነ አናጣውም፡፡
ይህ ማለት ግን በአንድም ሆነ በሌላ ምክንያት የህዝብ ሀብት ሲመዘበር መሽኮርመም አለብህ ማለት አይደለም፡፡ ኃላፊነትህ ሀገር እና ወገንን ከምዝበራ ማዳን እስከሆነ ድረስ በአብዛኛው በልመና እና በእርዳታ የምትተዳደር ሀገርን አሳልፈህ መስጠት የለብህም፡፡ በኢትዮጵያ ህዝብ ስም የሚመጣው የእርዳታ እና የልመና ገንዘብ የተለመነለትን አላማ ሳያሳካ የሚቀርበት ጊዜ እንዳለ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡
ይሄ ጉዳይ ደግሞ ከማንም በላይ ሊያሳምመው የሚገባው በኮሚሽነር አሊ ሱሌይማን የሚመራውን የፌደራል የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽንን ነው፡፡ እንደ እንጉዳይ እየበቀሉ የሚያድሩ ከሚመስሉት የአዲስ አበባ ዘመናዊ ህንፃዎች መካከል ምን ያህሎቹ ለሐሜት የተጋለጡ እንደሆኑ እናውቀዋለን፡፡
ይሄ ህንፃ እከሌ የተባለ ባለስልጣን ንብረት ነው፤ ያኛው ድርጅት የእገሌ ነው ለሚል የአደባባይ ሐሜት የተጋለጡ ንብረቶች መኖራቸው ፀረ ሙስና ኮሚሽንን እንቅልፍ ሊነሳው በተገባ ነበር፡፡ እንዲህ አይነቱ የአደባባይ ሐሜት ተመርምሮ እና ተጣርቶ ተጠርጣሪዎቹ ማግኘት የሚገባቸውን ቅጣት እንዲያገኙ ያስችላል በሚል ምክንያት የሐብት ማሳወቂያ እና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 ወጥቶ ስራ ላይ ከዋለ ሰነባብቷል፡፡ በነገራችን ላይ አዋጁ ወጥቶ ስራ ላይ ከዋለ በኋላ በመጀመሪያው አመት ማለትም በ2003 ዓ.ም 18ሺህ 94 ሰዎች ሐብታቸውን አስመዝግበዋል፡፡
ከነዚህም መካከል የኤፌድሪ ፕሬዚዳንት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት እና ፌዴሬሽን ም/ቤቶች አፈ ጉባኤዎች፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት፣ የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሀብታቸውን እንዳስመዘገቡ የፀረ ሙስና ኮሚሽን መረጃ ያመላክታል፡፡ ግን የትኛው ባለስልጣን ምን ያህል ሀብት እንዳለው ኮሚሽኑ ይፋ አላደረገም፡፡ ይህን ማድረግ እያለበት ያላደረገበት ምክንያት ነው ሊያነጋግር የሚገባው፡፡
የከፍተኛ ባለስልጣናቱ ሀብት መመዝገብ አንድ ርምጃ ነው፤ ዋናው ስራ ግን ሀብታቸውን ይፋ የማድረጉ ሒደት ይመስለኛል፡፡ አቶ በረከት ስምኦን፣ ወይዘሮ አዜብ መስፍን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ አባዱላ ገመዳ…ወዘተ ሀብታቸው እንደተመዘገበ ቢነገርም የሀብታቸው መጠን ይፋ አለመሆን ህብረተሰቡ ከሙስና የፀዳች ኢትዮጵያን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ውስጥ ሊጫወት የሚገባውን ሚና አዳክሞታል የሚሉ አስተያየቶች ይደመጣሉ፡፡
አቶ መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት ‹‹ዜጎች ከታችኛው አስከላይኛው መዋቅር የመንግስት አካል ድረስ ሙስና እንዳይኖር የሚያስችል ከባቢ መፍጠር አለባቸው›› ማለታቸውን አስታውሳለሁ፡፡ እኔ ደግሞ እንዲህ እላለሁ፡- ዜጎች እንዲህ አይነቱን ከባቢ መፍጠር የሚችሉት ፀረ ሙስና የመዘገበውን የባለስልጣናት ሀብት ለህዝብ ይፋ ሲያደርግ ነው እላለሁ፡፡
አንድ ባለስልጣን ካስመዘገበው ሀብት በላይ ሲቀማጠል ያየው ሰው ለሚመለከተው አካል ጥቆማ ሊሰጥ የሚችለው የባለስልጣናቱ ሀብት አስቀድሞ ይፋ ሲሆን ብቻ ነው፡፡ በተረፈ ጠንቋይ በመቀለብ ሙስናን መዋጋት አይቻልም፡፡ እንደ ፀረ ሙስና ኮሚሽን መረጃ ከሆነ ከላይ የጠቀስኳቸውን ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች ጨምሮ 393 ከፍተኛ ተሿሚዎች፣ 498 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ 10334 የሌሎች የመንግስት መስሪያ ቤቶች ተሿሚዎች እና የመንግስት ሰራተኞች፣ 3225 የአዲስ አበባ አስተዳደር ምክር ቤት አባላት ተሿሚዎች እና የመንግስት ሰራተኞች፣ 3644 የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ሰራተኞች በአጠቃላይ 18ሺህ 94 ሰዎች ሐብታቸውን ቢያስመዘግቡም፣ አሁንም ድረስ የመንግስት ኃላፊዎች ሀብት ምን ያህል እንደሆነ ጸረ ሙስና እና እግዜር ብቻ ናቸው የሚያውቁት፡፡ እንደው ፀረ ሙስና እግዜር ረድቶት የቱባ ባለስልጣናትን የሀብት መጠን ቢያሳውቀን ጥሩ ነበር፤ ደግሞም ያጓጓልም፡፡
የኃይለማርያም ደሳለኝ ሀብት ምን ያህል እንደሆነ ለማወቅ የማይፈልግ ሰው አለን? የበረከት ስምኦን እና የአዜብ መስፍን ሀብት ስንት እንደሆነ ማወቅ አያጓጓምን? የሌሎቹንም ባለስልጣናት ሀብት ማወቅ ከልብ አንጠልጣይ ፊልም በላይ ያጓጓል፤ ያቁነጠንጣል፡፡ እናም ፀረ ሙስና ኮሚሽን ሆይ ለመጓጓታችን ብቻ ሳይሆን ለፀረ ሙስና ትግሉ ስትል ጭምር የባለስልጣኖቻችንን ሀብት በፈጠረህ አሳውቀን፡፡ አለበለዚያ የፀረ ሙስናውን ትግል ራስህ እንደ ጀመርከው ራስህ እዛው ትጨረስዋለህ፡፡
ህብረተሰቡን የትግሉ ተሳታፊ ማድረግ የሚቻለው፣ ትግሉ በድል እንዲጠናቅ የሚያስችሉ መረጃዎችን ይፋ በማድረግ ነው፡፡ ነገር ግን ኮሚሽኑ መረጃዎቹ ላይ አንጥፎ ተኝቶ ህብረተሰቡ የነቃ የፀረ ሙስና ትግል እንደሚያካሂድ መመኘት እንደማሞ ቂሎ ፍሬ አልባ መሆን ነው፡፡ የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አሊ ሱሌይማን የባለስልጣናቱን የሀብት ምዝገባ መረጃ በአጭር ጊዜ ውስጥ ይፋ በማድረግ አባክዎን ትግሉን ያጧጡፉ!!!

የአባ በላ ፍቅር እስከ መቃብር (ማህሌት ነጋ)

0
0

በማህሌት ነጋ

“ሃይለማሪም ደሳለኝ አብዩዝድ ነው። እንደውም ማታ ማታ (በህወሃቶች) ሳይገረፍ አይቀርም!” ብሎ ነበር ብርሃኑ ዳምጤ ከጥቂት ወራት በፊት በፓልቶክ ላይ።….
Aba Mela
“ስለ አንድ ሰው ስንጽፍና ስንናገር ቢቻል አዎንታዊና መልካም ከሆኑ ነገሮች መጀመር ጥሩ ነው” ይሉ ነበር “የኔታ” በሚል ቅጽል ስም እንጠራቸው የነበሩ የዘጠናኛ ክፍል የአማርኛ አስተማሪያችን። ቀጭንና የዋህነት የተላበሰ ፊታቸው ላይ ችፍ ብሎ የማርክስን ግርማ ሞገስ ያጎናጸፋቸውን ገብስማ ሪዝ በእጃቸው እየዳበሱ ያስተማሩኝ ትዝ አለኝ።

ነገሩ የድሮ ትምህርት ቢሆንም የተማርኩትን በማሰብ እንደ አዞ ደንዳና ቆዳ ስለ ታደለው ብርሃኑ ዳምጤ ለመጻፍ ስነሳ ከልቅ አፉ ባሻገር ከማደንቅለት ባህሪው ብጀምር መልካም ነው ብዬ አሰብኩ።

ማንም በቀላሉ ሊክደው የማይችለው ሃቅ ብርሃኑ ዳምጤ (አባ መላ) የፍቅር ሰው ነው። ብርሃኑ ለፍቅር ሲል ብዙ መስዋእትነት ከመክፈል አልፎ በስደት ዘመኑ ሳይቀር እንደ ዘላን ብዙ ተንከራቷል። የሚገርመው ነፍስ ካወቀ ጀምሮ እስካሁን ያፈቀረው አንድ ብቻ ነው። ለፍቅረኛው ሲልም ብዙ ተሰቃይቷል፣ ወደ ፊትም መሰቃየቱ አይቀሬ መሆኑን ለመተንበይ ቀላል ነው።

ታዲያ ብርሃኑ “ሆዴ! ያላንቺ ማን አለኝ!” እያለ በፍቅር የሚያቆላምጣት አይኗ የሚያማልሉ፣ አፍንጫዋ ሰልካካ፣ ጸጉሯ የሃር ነዶ የሚመስሉ የቆንጆ ቆንጆ የሆነች ኮረዳ እንዳትመስላችሁ። በተቃራኒው፣ አፍንጫም፣ አይንም የሌላት ትልቅና ወደፊት የተገፋ ጆንያ የሚመስል ግንባር ብቻ ያላት መሆኗን ጠንቅቆ ያውቃል። ያለባት አንድ ትልቅ ችግር የመኖ ነገር አይሆንላትም። በቀላሉ አትጠረቃም። ቢሆንም ነፍሱ እስኪወጣ ይወዳታል።

በፍቅር “ሆዴ! ሆዴ! ” የሚላትም ሌላ ሳትሆን በስተርጅና አክሮባት የምታሰራው ሆዱን ነው።

“ሆድ፣ ሆዴ! ያላንቺ ማን አለኝ!” እያለ ዘውትር በፍቀር የሚዳብሳት ፍቅረኛ። የሚያቃጥል ፣ የሚያንቀዠቅዥ፣ ህሊና የሚያስት ፣የሚያክለበልብ፣ ቀልብ የሚያሳጣ ከሁሉም በላይ የሚያዋርድ የሆድ ፍቅር ቢባል ማጋነን እንደማይሆን እርግጠኛ ነኝ።

የታደለ ለነጻነት፣ ለፍትህ፣ ለእኩልነት፣ ለሰላም መስዋእትነት ሲከፍል፣ በየእስር ቤቱ ሲሰቃይ የቁብና የእድር ዳኛ ለመሆን ብቃት የሌለው አጭቤ ግን በሆድ ፍቅር ተቃጥሎ የሆድ ማንዴላ ሆኖ እንደ ረከሰ ሴተኛ አዳሪ በየአደባባዩ ከንቱ ስብእናውን በስሙኒ እየቸረቸር ለከፈሉት ሁሉ እየደነሰ ይኖራል። ኑሮ ካሉት…መሆኑ ነው።

ታዲያ ሰሞኑን ከተቃዋሚ ጎራ አመለጥኩ እያለ እያለከለከ ቤን (ሆድፈርስት) እና ሰለሞን ቅንድቡ በተባሉ እርካሽ የሆድ ውጠራ የትግል አጋሮቹ በኩል የለመደውን ቱሪናፋ ሲቸረችር አያቴን አስታወሰኝ። አፈሩ ይቅለላትና አያቴ የአባ መላ አይንቱን የመለፍለፍ ልክፍት ያለበትን ቅል ስታይ “አሻሮ የበላ አሻሮ ያገሳል” ነበር የምትለው።

እውነት ለመናገር ነገሩ ሁሉ ብርሃኑ መኖ ፍለጋ መጣ መኖ ፍለጋ ተመለሰ ወይንም ተገለባበጠ መሆኑን ስለምናውቅ እራሱን ማግዘፍ ያልተሳካለት ምስኪን ሆድ ወዳድ ምን ቢናገር ሊያስከፋን አይችልም። በነገራችን ላይ አባ መላ የሚለው ስም ስለሚያንስበት ከዚህ በኋላ አባ በላ በሚል የማእረግ እድገት እዲሰጠው ፍቃዳችሁ ይሁን።

አንድ ምስክር እንዳለው አባ በላ መብላት የሚያቆመው ሲጠግብ ሳይሆን ሲደክመው ብቻ ነው። ታዲያ አባ በላ በመፈረካከስ ላይ ካለው ከወያኔ መንደር አምልጬ መጣሁ ብሎ እያለከለ እንደመጣ መጀመሪያ ያቀረበው ጥያቄ የመኖ ነበር። “ይከፈለኝ” አለ። ለከፋዮቹ ችግር የሆነው ምን ሰርቶ ምን እንደሚከፈለው ማጣራት ነበር። ከፓርክንግ ሎት ምንተፋ ባሻገር ሙያ የለው፣ ትምህርት የለው፣ እውቀት የለው፣ አመል የለው፣ ግብረገብ የሌው፣ ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ነበር።

የመጣው ባዶ እጁን ግን ደግሞ ትግስት የሌለው ቀዥቃዣ ቢሆንም “ሆደ ሰፊ” መሆኑ የታወቀ ጉዳይ ነው። ይከፈለኝ ሚስጥር ይዤ መጥቻለሁ፣ የወያኔ ሰላዮች በአሜሪካና በአውሮፓ ስምዝርዝርና አድራሻ አለኝ አለ። በርግጥ ለዚህ ጠቃሚ መረጃ ክትፎ ምናምን ተገዝቶለት መረጃውም ለሚመለከታቸው የአሜሪካና አውሮፓ መንግስታት መመራቱን ሰምቻለሁ።

በኢሳት ላይ ካልወጣሁ፣ መድረክ ካልሰጣችሁኝ አለ። የሚገርመው ግን በኢሳት ላይ ቃለምልልስ ለማድረግ እንኳን ይከፈለኝ አለ። ኢሳቶችም ለዚህ አንከፍለም አሉት። ምንም እንኳን መጀመሪያ ይከፈለኝ ሲል የቀረበው በስካይፕ ቢሆንም ቢያንስ ለትራንስፖርት ይከፈለኝ አለ።። የሆድ ነገር፣ የሆድ ፍቀር፣ የሆድ ትግል ነው ነገሩ ሁሉ።

የተቃዋሚው ጎራ አስቸጋሪ ትግል እንጂ መኖና አረቄ እንደሌለው ሲገባው ነገሩ ሁሉ ሊጥመው አልቻለም። እርሱ ሃሳቡ ሁሉ በቀላሉ የማትረካውን ፍቅረኛውን “ሆዴን!” ሞልቶና ሸንግሎ ማሳደር ነው።

ያም ሆነ ይህ ስለ አባ በላ ብዙ መጻፍ አያስፈልግም። ጓዙን ጠቅልሎ፣ ሆዱን ታቅፎ እያለከለ በመጣበት መንገድ ሄዶ የድሮ ጌቶቹ እግር ስር እያለቀሰ ማሩኝ ቢልም እኛ ድምጹን ቀርጸን ስላስቀረን ይሂድ ተውት። ድሮም ቢሆን ጅብ በጨለማ እንጂ በብርሃን ኑሮ አይሳካለትም።

ያልተማረው ተንታኝ አባ በላ እንደ ጀብድ የሚቆጥረው ስራ ፈቶ ፓልቶክ ላይ ተጥዶ የቆጥ ያባጡን መቀባጠሩን ነው። ለማንኛውም አባ በላ መንግስት የለም ወያኔ አልቆለታል እያለ ከዘፈናቸው ዘፈኖች መሃል አለፍ አለፍ እያልን እናዳምጥ። ወጪት ሰባሪ የሆነው አባ በላ ጌቶቹን የሚያጋልጡ በርካታ ዘፈኖች ስለዘፈነ ቀስ በቀስ እያወጣን እንዝናናባቸዋለን። እነዚህን ከታች ለናሙና የመረጥኳቸውን የውስጥ አዋቂው የአባ በላን ንግግሮች (ዘፈኖች) በጥሞና ይከታተሉ።

ሃይለማሪያም ደሳለኝ “አብዩዝድ” ነው
Haile-Mariam-Desalegn
ይለማሪያምን ተዉት፣ እኔ ለሃይለማሪያም ማዘን ጀምሪያለሁ። እኔ እንደውም ከሳውዲ ከተመለሱት ሰዎች አንዱ ይመስለኛል። ምክንያቱም የት ጠፋ ይሄ ሰውዬ። በሳውዳአረዲያ ነበረ ማለት ነው። እና ሰሞኑን እንሰማለን ማለቴ ነው። አንዱ abused የሆነ ሰው ነው ማለቴ ነው። እርሱ እኮ ሰልፍ ሊወጣለት የሚገባው ሰው
ነው። ግን ጥሪ ለምን እንደማያቀርብ አይገባኝም። አለ አይደለም እንደዚህ abused እደረጋለሁ፣ እንደውም ማታ ማታም ሊገረፍ ይችላል። ምክንያቱም በጣም
ተደነባብሯል።

የሚያወራው ነገር ሁሉ ግራ የሚያጋባ ነገር ነው። እርሱን ተዉት እንደ መሪም አትቁጠሩት። እሱ እንደ ሰው ህሊና ቢኖረው immediately resign ማድረግ
አለበት። እውነቴን ነው፣ ከልቤ ነው። መናቄ አይደለም። ምክንያቱም authority ሲባል de facto power ሊኖረው ይገባል። ዝምብሎ መቀለጃ ስትሆን፣ you have to resign። ብዙ ስራ አለ ለሱ የሚሆን። ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ የኮብል ስቶን ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አለ። አንዱን ሊመራ ይችላል። በደቡብ የሚካሄደውን የኮብል ድንጋይ ምንጣፍ ቢከታተል ይሻለዋል። ምን አጨቃጨቀው ከነዚህ ሰዎች ጋር።

ሳሞራ ዘረኛ ነው

Samora (2)

አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ስትመለከት structurally እከሌ ሚኒስትር ነው ይሉሃል ምክትሉ ደግሞ ሌላ ሰው ነው። ዋነው ሰውዬ አይደለም አለቃው፣ ምክትሉ ነው አለቃው። እኔ በቅርብ ቦታውን አልጠቅስልህም የመከላከያ ሚኒስትሩ እዚህ መጥተው ነበር፣ ዋሺንግተን ዲሲ። አብሯቸው ኢታማዦር ሹሙ ሳሞራ ነበር።

የውጭ አገር ሰዎች ሁሉ ያሉበት ዲነር ነው። ሌሎችም ባለስልጣኖች ነበሩ። እኔም ነበርኩ። ኢታማዦር ሹሙ መከላከያ ሚኒስቴሩን ይሰድበዋል፣ በዘሩ። ፈረጆች ባሉበት እኮ ነው። ቀለድኩ ነው የሚለው። እንዲህ አይነት ቀልድ አለ እንዴ። በወታደራዊ ስርአት ውስጥ መከላከያ ሚኒስቴር ማለት ትልቅ power ነው ያለው።

አንተ አስር አለቃ ሆነህ ሃምሳ አለቃው ሲመጣ ቆመህ ነው ሰላምታ የምተሰጠው… አንድ ኤታማዦር ሹም፣ምንም ልምድ የሌለው ጎሬላ ነው። በጣም ጨዋ ሰው
ነው መከላከያ ሚኒስቴሩ፣ እኔ ስለማውቀው ነው። በጣም ነው የተናደደው (አቶ ሲራጅ ፈርጌሳ)። ደሞ እኮ አስተርጉሞ ለፈረንጆች ሊነግራቸው ይፈልጋል። ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዘናዊ አሉ ብሎ ነው የሚያወራው። የዚህን ሰውዬ ብሄረሰብን እንደ ሌባ አድርጎ ነው ይሚቆጥረው።…እኔ እንደዛን ቀን ደሜ ፈልቶ አያውቅም።

ብዙ ሰዎችም የሚያውቁት በብዙ ነገር ነው፣ የኢትዮጵያ ህዝብ አንዱ መቼም የሚፋረደው እሱን (ሳሞራን) ነው። በመከላከያ ውስጥ የተጠላ ሰው ነው። ይሄንን ሰውዬ ሲያዋርደው ስታይ really በዚያን ለት ዲነሩ አንዳለ ነው የተበላሸው…። አንተ ሚኒስቴር ስለሆንክ አይደለም ዘበኛው (ህወሃት ከሆነ) ሊኒቅህ ይችላል።…አንድ ስርአት structural problem ካለብት ሚኒስቴሩን ሹፌር የሚያዘው ከሆነ…አሁን እዚህ ዋሺንግተን ኤምባሲ አንድ ሰለሞን የሚባል ሃያ አመት የሚያውደለድል አለ። ምን እንደሚሰራ አይታወቅም፣ ።።ሰላይ ነው ልጁ መሰለኝ…ሰላሳ አምባሳደር ይቀያየራል። እርሱን የሚነካው የለም። ሾፌር ነው መደበኛ ስራው። ግን he is powerful than the ambassador, even ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ የበለጠ። እንደዚህ አንደዚህ አይነት ሰዎች ናቸው እዚህ የሚመደቡት።….

አዜብ መስፍን አጭበርባሪ ናት
azeb

ባክህ ተው አዜብ ምናምን ይለኛል። በሶስት መቶ ብር፣ በሁለት መቶ ብር ነው የምኖረው ምናምን ትላለች። ያልጠየቋትን ትለፈልፋለች። በሁለት መቶ ብር ነው እንዴ አሜሪካ በየግዜው የምትመጣው። ምን አይነት የምን ገንዘብ ነው? እኔ እሱ አይደለም፣ ስለሱ ችግር የለብኝም።…ይሄንን የሚገዛ ሰው ካለ ይግዛ stupid ሰው ካለ እንጂ አራት ሺ ብር ደሞዝተኛ የ100ሺ ብር ቦርሳ የምትገዛ ሴትዮ “አራት ሺ ብር ምናምን” ትላለች። በቃ ይሄው ነው።

First of all, የምትሰጣቸው ኮሜንቶች backfire የሚያደርግ ነው። መለስ መንጃ ፍቃድ የለውም፣ ባንክ አካውንት የለውም …ምን ማለት ነው? ቤተሰቡን take care የማያደርግ ፍጡር ምን አይነት መሪ ነው? እንዴት ነው መንጃ ፈቃድ የሌለው መሪ የሚኖረው በአለም ላይ?…እንዴት ነው ባንክ አካውንት የሌለው መሪ የሚኖረው? ይሄ irresponsibility ነው። ቤለሰብህን handle ማድረግ አለብህ…. መታወቂያ ሊኖርህ ይገባል። መታወቂያ የሌለው መሪ ነው እንዴ ሲመራ የነበረው። ምንድን ነው የሚያወሩት?…ስለገንዘብ የማያውቅ መሪ ነው?… እንዴት ነው ስለገንዘብ የማያውቅ ሰው ስለሃገር ኢኮኖሚ ሲወስን የነበርው? ይሄ ጥሩ ነገር አይደለም። ለማን ተይ እንዳላሏት አልገባኝም።

እሷ ገንዘብ የሚመስላት በቼክ የሚሰጥ ነው። How about የቤተ መንግስት ኦዲት የማይደረገው ገንዘብ…እማይወራረድ ገንዘብ አለ፣በሚሊዮን የሚቆጠር። ገንዘብ ሚኒስቴር የማያውቀው። እሱ ገንዘብ አልመሰላትም እንዴ?….How about ኤፈርት? የኤፈርት ስራ አስኪያጅ አይደለችም እንዴ?… ስለዚህ እንደዚህ አይነት ነገር ያመኛል። እንደዚህ አይነት childish የሆነ ፉገራ። እንደ ሃገር ደግሞ ሊያመን ይገባል።…አውቃለሁ የዚህ የዶክተር ጌታቸውም ጠበቃ እርሷ ነች። I know that, አጭበርባሪ ነች። የኢህአዴግ ዘጠነኛ ጉባኤ አድርባይነትን ተዋጉ ብሎናል ይሄ ሩም በአር ያነት እራሱን አስቀድሞ በአድር ባይነት ላይ ዘመቻ አውጇል።

የአቋም ለውጥ

ታዲያ ዛሬ አባ በላ ግርማ ብሩ አሞሌ ጨውና ብር ሲያሳየው እንደልማዱ ከሻቢያ አምልጨ ተመለስኩ እያለ ልፈፋ ጀመረ። አይ አባ በላ! በኢሳት ላይ በግንባር ሲቀርብ ሲሳይ አጌና “ከወያኔ ካምፕ ምን አስወጣህ?” ብሎ ሲጠይቀው ደረቱን ነፋ አድርጎ “ህሊናዬ እንቅልፍ ነሳኝ” አለ።

በረጅም አረፍተ ነገርም እንዲህም አለ፣ “በየግዜው የምናያቸው ነገሮች እየተሻሻሉ መምጣትን ሳይሆን እጅግ በሚያሳዝን ሁናቴ በአገሪቱ ኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ፣ ማህበራዊ ህይወት ውስጥ በተለይ ዲሞክራሲን ፍትህን፣ የመልካም አስተዳደር ችግር፣ የሰብአዊ መብት ጥሰት ህሊናህ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ እየሆነ ሲመጣ ፣አገሪቱ የጥቂቶች ሆና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ባእድ ሆነው፣ ወጣቶች ሌት ተቀን ከዛች አገር እግራችን ይውጣ በሚል አገራቸውን እስከሚጠሉበት፣ ሴት እህቶቻችን በየአረብ አገሩ በሚሸጡበት፣ ጋዜጠኞች በመጻፋቸው እድሜ ልክ በሚፈረድበት፣ የኑሮ ውድነት በአለም ደረጃ ፍጹም ልትሸከመው በማትችል ደረጃ፣ ዛሬ ኢትዮጵያዊ ውስጥ የመንግስት ሰራተኛ እንዴት አድርጎ እንደሚኖር ሁሉ የማያውቅበት ሁናቴ ሲፈጠር ያንን ጉዳይ እንዲታረም ባለን ‘አክሴስ’ ሃላፊዎቹን ሁሉ እንትን ማድረግ እንሞክር ነበር።….ስር አቱ እርስበርስ መናበብም አልቻለም።….በጣም እሮሮ ያለብት ስርአት በመሆኑ ከዚህ መንግስት ጋር ሆነህ ለማስተካከል የምታደርገው ጥረት ዝም ብሎ ግዜ ማጥፋት ስለሚሆን እንደውም በሚሰራው ስተትና ወንጀል ላይ ታሪካዊ ሃላፊነት ይኖራል የሚል እንትን ስላለኝ ካለብኝ የዜግነትና የሞራል ጉዳይ አንጻር ጥያቄው አገር የማስቀደም፣ ህዝብን የማስቀደም ጉዳይ ስልሆነና የግል ጉዳይ ስላልሆነ የግዴታ ይህንን ስርአት በማንኛው መልክ ለማስተካከል ወይንም ለመለወጥ ከሚታገሉ ጎራ ዲሞክራሲያዊ ሃይል ጋር አብሮ መስራቱ ለአገር ይጠቅማል የሚል እምነት ላይ ደርሻለሁ። እና አሁን ሲሪየስ አቋም ነው ያለኝ።….”

“መቼም ይሄ በረጅሙ “በጄጄጄ!” የሚያስብል ጉዳይ ቢሆንም አያቴ “ጦጣ መንና ጫካ ገባች” የምትለው ተረቷን አስታወሰኝ።

አባ በላም ዝም ብሎ ህሊናዬ እንቅልፍ ነሳኝ የሚል ጨዋታ ጀመረ እንጂ አፈጣጠሩ ለህሊና ሳይሆን ለሆድ ስለሆነ ብዙ በአደባባይ መለፍለፉን ትቶ ሆዱን እየጠቀጠቀ ቢኖር ይመረጣል። እኔን ከአባ በላ በላይ የሚያሳዝኑኝ “የጨነቀው እርጉዝ ያገባል” እንዲሉ እርኩስ ጥንባቸውን ያወጣ ሆድ አደር ድጋሚ መቀጠራቸው ነው። ሳሞራ ዘረኛ፣ ሃይለማሪያም እርባና ቢስ አሻንጉሊት፣ አዜብ አጭበርባሪና ሙሰኛ፣ ስብሃት ሰካራምና ሴሰኛ፣ ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ሌባ፣አባይ ወልዱን መሃይም፣ ቴድሮስ አድሃኖም ህጻንና እንጭጭ፣ ሽመልስ ከማል የማይረባ አድርባይ፣ አባ ዱላ ላንቲካ፣ ግርማ ብሩ እግር አጣቢ፣ በረከት ሴሰኛ….እያለ ፓልቶክ ላይ እንዳልጨፈጨፋቸው ዛሬ ሻቢያን ለመዋጋት ተመልሼ መጣሁ እያለ ያጃጅላቸዋል።…

አባ በላ ጠመዝማዛ መንገድ በከንቱ ተጓዘ እንጂ እውነታው እንዲህ ነው። የእርሱ ፍቅር እስከ መቃብር እንደነ ሰብለወንጌል የፍቅር ታሪክ የሚያማልል አይደለም። አባ በላ የሚያፈቅረው አብሮት የተወለደውን ሆድ ስለሆነ ጥቂት ቆይቶ አብሮት ይቀበራር። እኛም የሆድ ፍቅር እስከ መቃብር የሚለውን ታሪኩን ጽፈን የቀብሩ ስነስርአት ላይ እናስነብብለታለን። ምስኪን የሆድ አርበኛ! ስለ ህሊና ሳትናገር ዝም ብለህ የሰጡህን መኖ ጠቅጥቅ። መልካም መኖ ይሁንልህ ብለናል!


ጋዜጠኞች ላይ ያለ ማስረጃ የሚሰነዘሩ ውንጀላዎች ባስቸኳይ እንዲቆሙ እንጠይቃለን!

0
0

ከኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) የተሰጠ መግለጫ

ማህበራችን ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዶ የምዝገባ ሰርተፊኬት ለማግኘት የጀመረው እንቅስቀሴ በቅርቡ ከመንግስት አወንታዊ ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ በማድረግ የተቋቋመለትን አላማ ለማሳካት እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን መብትና ጥቅም ከማስጠበቅና የመናገር ነፃነትን ከማበረታታት ባለፈም ከአህጉራችን አፍሪቃ ጋዜጠኞች ጋር በመተባበር የመላው አፍሪቃ ጋዜጠኞችን መብትና ጥቅም የሚያስጠብቅና የመናገር ነፃነትን የሚያበረታታ አህጉራዊ ተቋም ለመመስረት ተነሳሽነትን ወስዶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ በቅርቡም የምስራቅ አፍሪቃ ጋዜጠኞችን በማስተባበር አህጉር አቀፍ እንቅስቃሴያችንን ለማስጀመር ዝግጅት እያደረግን ነው፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተግባር ጋዜጠኛውን ሳይወክሉ የጋዜጠኛውን ስም የያዙት የኢጋማ፣ የኢነጋማና የኢብጋህ አመራሮች ነን የሚሉት ግለሰቦች በመቀናጀት በየሚዲያው እየቀረቡ ጋዜጠኞችንና የሚዲያ ተቋማትን ለማሸማቀቅ ያለመ ውንጀላና አሉባልታ የመንዛት ዘመቻ ጀምረዋል፡፡ ግለሰቦቹ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ቀርበው በጋዜጠኞች ላይ ከሽብር ፈጠራ እስከ ሀገር ማተራመስ የደረሰ የውንጀላ መዓት ቢደረድሩም አንዳችም ማስረጃ አላቀረቡም፡፡

ለምሳሌ የካቲት 22 ቀን 2006 ዓ.ም በታተመው አዲስ አድማስ ጋዜጣ (ቅጽ13 ቁጥር 737) ላይ ስማቸውን ደብቀው ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ጋዜጠኞች ሀገር ለማተራመስና ሽብር ለመፍጠር እየተዘጋጁ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ይሁን እንጂ “ምን ማስረጃ አላችሁ” ለሚለው የጋዜጠኛዋ ጥያቄ የመለሱት “እኛ እና እነሱ እንተዋወቃለን፡፡” የሚል አስገራሚ መልስ ነው፡፡ ይህ መሰረተ ቢስ ውንጀላ ጋዜጠኞችን ለማሸማቀቅ የተወረወረ በመሆኑ የኢጋማ፣ የኢነጋማና የኢብጋህ አመራሮች ነን የሚሉት ግለሰቦች ጋዜጠኞችን እና የሚዲያ ተቋማትን ያለ ማስረጃ መወንጀላዎች ባስቸኳይ እንዲያቆሙ ይጠይቀል፡፡

በመቀጠልም በሪፖርተር ጋዜጣ (የዕሁድ እትም ቅፅ 19 ቁጥር 1446) የካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም “ኢጋማ በምስረታ ላይ ያለውን የጋዜጠኞች መድረክ አስጠነቀቀ” የሚል ዜና ተመልክተናል፡፡ ሆኖም በጋዜጠኞች ስም ተሰባስበው ጋዜጠኛውን የሚጠቅም አንዳች እንቅስቃሴ ሳያደርጉ ከመተኛታቸው ብዛት አልጋቸው ለረገበ ማህበራት ማስጠንቀቂያ ምላሽ በመስጠት ጊዜ በመሆኑም ምለሻችን በዝምታ መስራት ነው፡፡

የግለሰቦቹ የውንጀላ ንግግር የሚያስረዳው ከህግ፣ ከሞራል እና ከሙያዊ ስነምግባርም በላይ ራሳቸውን ለመሾም የሚፍጨረጨሩ መሆኑን ነው፡፡ ግለሰቦቹ በተለያዩ ጊዜያት መንግስት የፕሬስ ተቋማት ላይና ጋዜጠኞች ላይ የወሰዳቸውን ኢ-ህገመንግስታዊ እርምጃዎች እንደ ጋዜጠኛ ማህበር መሪ ከመኮነን ይልቅ የመንግስትን እርምጃ ሲያወድሱ ተስተውለዋል፡፡ በተጨማሪም በእስር ላይ ሆነው ህክምና በመከልከላቸው ለከፋ ስቃይ ስለተዳረጉ ጋዜጠኞችም ትንፍሽ ሲሉ አልታየም፡፡

እነዚህ የጋዜጠኛ ማህበራት መሪዎች ነን ያሉት ግለሰቦች እንደማህበር መሪ ሳይሆን እንደ ስለላ ተቋም ጋዜጠኞች እና አንዳንድ የሚዲያ ተቋማት ሃገር ለማተራመስና የሽብር ጥቃት ለመፈፀም እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ መረጃ እንዳላቸው በይፋ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም

1ኛ. የሶስቱ ማህበራት መሪዎች አለን የሚሉትን መረጃ ለመንግስት በአፋጣኝ ሳይሰጡ መቆየታቸው በሀገራችን ህግ መሰረት ሊጠየቁው እንደሚገባ እንዲሁም

2ኛ. የሶስቱ ማህበራት መሪዎች በጋዜጠኞች እየተቀነባበረ ነው ካሉት የሽብርና ሀገር የማተራመስ እንቅስቃሴ ጀርባ እንዳሉ የጠቀሷቸውን ኤምባሲዎች በግልፅ ጠቅሰው ለመንግስት እና ለህዝብ እንዲያስታውቁ እንጠይቃለን፡፡

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ)

መጋቢት 10 ቀን 2006 ዓ.ም

በኑሮ ውድነቱ እየተባባሰ መምጣት ኢሕአዲግ እና ሕዝቡ ይበልጥኑ ሆድና ጀርባ ሆነዋል

0
0

ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ

የኢህአዲግ ወያኔ መንግስት የስልጣን ወንበር በትሩን በሀይል ከተቆናጠጠበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ ሕዝብ የአኖኖር ሁኔታ ከእለት ወደ እለት እያሽቆለቆለ እና እየወረደ በመምጣቱ ሕዝቡ ከምቼውም ጊዜ በበለጠ በአሁኑ ወቅት ኑሮን መቋቋም በማይችልበት አደገኛ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኝ እና በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የኑሮ ውድነት ተቋቁሞ መኖር ከባድ ፈተና እየሆነባቸው እንደሆነ የችግሩ ሰለባና ተጠቂ የሆኑት ሰዎች በየጊዜው ከሚያሰሙት ሮሮና ጩኸት መረዳት ይቻላል::ይህንንም እየተባባሰ እና እየጨመረ የመጣውን የኑሮ ውድነት ተከትሎ የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን ስራ አስፈፃሚ የተቃውሞ ሰልፍ ሊጠራ እንደሆነ ታውቋል:: የአንድነት ፓርቲ ሊጠራ ባሰበውና በታቀደው ሰላማዊ ሰልፉም ላይ በስርዓቱ እና በኑሮ ውድነቱ የተማረሩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በነቂስ በመውጣት በምሬት የታመቀ የብሶት ድምጻቸውን በወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ላይ እንደሚያሰሙ ይጠበቃል:: በአሁኑ ወቅት ጥቂት የስርአቱ ደጋፊዎች እና የወያኔ ካድሬዎች ካልሆኑ በስተቀር በኑሮ ውድነቱን የተነሳ ተጎጂ ያልሆነና ሕዝቡ ኑሮን መቋቋም በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ በመገኘቱ ስርዓቱን የማያማርር የህብረተሰብ ክፍል የለም ብል ማጋነን አይሆንብኝም ::

hrr2የወያኔ መንግስት የሚያራምደው ፖሊሲ የመላው ኢትዮጵያን ሕዝቡ ፍላጎት እና ጥቅም ማዕከል ያላደረገ ሲሆን የተወሰኑን የህብረተሰብ ክፍሎችን ብቻ ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል :: መላውን የኢትዮያ ህዝብ እና ክልል ተጠቃሚ ያላደረገው የመንግስት የልማት ስትራቴጂ ፖሊሲ እና በመላው ሀገሪቱ ላይ በስፋት ተንሰራፍቶ ያለው ሙሰኝነት ከእለት ወደ እለት የሕዝቡ የአኖኖር ሁኔታ እያሽቆለቆለ እና እየወረደ እንዲመጣ ካደረጉት ምክንያቶች ውስጥ ተጠቃሽ ሲሆኑ ለኑሮ ውድነቱ ግንባር ቀደም ተጠያቂው መሆን ያለበት ሀገሪቱን እየመራው እና የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት በፍጥነት እያሳደገ እንዳለ የሚያወራው የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ነው:: በነገራችን ላይ የኢህአዲግ መንግስት በየጊዜው ስለ ሀገሪቷ ኢኮኖሚ እድገት የለመደውን የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ይለፍልፍ እንጂ ይህን በፍጥነት እያደገ ነው ብሎ ወያኔ የሚያወራለትን የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ እድገት በተመለከተ የተባለው እድገት ከወረቀት ኣልፎ መሬት ላይ የሚታይ ነገር የለም የሚሉ ሰዎች በብዛት የሚገኙ ሲሆን ይህም ሀሳብ እኔንም ጨምሮ ብዙዎች የሚስማሙበት ጉዳይ ነው::

hr3ታስታውሱ እንደሆነ የወያኔ ቁንጮ የነበረው ሟቹ የቀደሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት በአሥር አመት ዉስጥ «ኢትዮጵያ በምግብ እራሷን ትችላለች። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በቀን ሶስቴ እንዲመገብ እናደርጋለን» ብለው ነበር ነገር ግን ይህ የአቶ መለስ ዜናዊ ንግግር የውሃ ላይ ሽታ ሆኖ ቀረ :: በአንጻሩ አቶ መለስ የኢትዮጵያን ሕዝብ በቀን ሶስቴ እንዲመገብ እናደርገዋለን ያሉለት ኢህአዲግ ኢትዮጵያን በብቸኝነት በሀይል መግዛት ከጀመረ ወደ 23 አመታት እየተጠጋ ሲሆን በእነዚህ አመታቶች ውስጥ ምንም የተለወጠ ነገር የለም:: የወያኔ መንግስት በተቆጣጠረው በመገናኛ ብዙሃን እንደሚለፈልፉት የኢትዮጵያ ኢኮነሚው ዕድገቱ በፍጥነት ሽቅብ እየገሰገሰ ሳይሆን ወደታች እያሽቆለቆለ ይገኛል:: ምናልባት የኢኮኖሚ እድገቱ በወረቀት ስሌት ላይ ኑሮ እጅግ መራራ ከመሆኑ የተነሳ የሰዉ የአኖኖር ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ ዉስጥ ዉስጡን የሚያልቁት ወገኖቻችን ብዛት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነዉ።በአሁኑ ሰአት ሕዝቡን የውሃ እጦት፣ የመብራት እጦት፣ የኔት ዎርክ ችግር፣ የትራንስፖርት እንደሚፈልገው አለማግኛት በአጠቃላይ ችግሩ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ በከፍተኛ ሁኔታ ተባብሶ ቀጥሏል:: በይበልጥ የአዲስ አበባን ነዋሪ ክፉኛ ምሪት ውስጥ አስገብቶታል::

በአዲስ አበባ ሕዝቡ ታክሲ ለመያዝ በወረፋ ላይ

በመላው አገሪቱ አዲስ አበባን ጨምሮ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣው የውሃ፣የመብራትና የቴሌኮም አገልግሎት ጥራት መጓደልና የአገልግሎት መቋረጥ እንዲሁም በአገሪቷ እጅግ ከፍተኛ የሆነ የዉጭ ምንዛሪ እጥረት እየታየ ሲሆን በሀገሪቱ ላይ በደረሰው በኢኮኖሚ ችግር የተነሳ ሕዝቡ ያለውን የኑሮ ውድነት መቋቋም በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ በመገኘቱ ነገሮች እየከረሩ በማንኛውም ጊዜና ሰሀት ግባታዊ ሕዝባዊ አመጽ ሊነሳና ትልቅ ችግር ሊፈጠር እንደሚችል የሚሰጉ ብዙዎች ናቸዉ።

በአሁኑ ሰአት እንደሚታየው እና መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥን ይፈልጋል ህዝቡ ሀገሪቱን እየመራ ባለው የወያኔ መንግስት ለመመራት ፍቃደኛ አይደለም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ሮሮ በማሰማት ላይ ይገኛል:: በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያ ውስጥ ከየቦታው የሚሰማው እና የሚታያው የሰበዓዊ መብት ረገጣው አፈናና ግድያው ከጊዜ ወደ ጊዜ ተባብሶ እየቀጠለ ባለበት ሁኔታ በየቀኑ እያሸቀበ የመጣው የኑሮው ውድነቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ጋር ሆድ እና ጀርባ ሆነው እንዲቀጥሉ እያደረጋቸው ሲሆን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ የሕዝቡ ንዴትና ቁጣ በከፍተኛ ሁኔታ በመፋፋም ላይ ይገኛል::

ከዚህም የተነሳ መንግስት በየቀበሌው፣በየመስሪያ ቤቱ በሚጠራቸው ማንኛውም ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ለመገኛት ሕዝቡ ፍቃደኛ እና ደስተኛ አይደለም:: ስለዚህም የሕዝቡ ከመንግስት ጋር ሆድና ጀርባ መሆን የወያኔን መንግስት ክፉኛ ጭንቀት ውስጥ የከተተው ጉዳይ ሲሆን በመሆኑም ለመጪው 2007 ለሚደረገው ምርጫ የሕዝቡ በመንግስት ላይ ያለው ጥላቻ እየጨመረ መምጣት እራሱን የቻለ አስተዋጽኦ ሊኖረው እንደሚችል በብዙዎች ዘንድ ይገመታል::

በአዲስ አበበ የውሃ ወረፋ

የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ባለስልጣኖች በሚቀጥለው አመት ምርጫ የሕዝቡን ድምጽ እንደማያገኙ በሚገባ ቢረዱትም ነገር ግን የለመዱትን የማጭበርበር እና የሌብነት ልምዳቸውን በመጠቀም ለቀጠይም አመታት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የበላይ በመሆን ሕዝብን እየጨቆኑና እየረገጡ ለመኖር የሚያስችላቸውን ስትራቲጂ በመንደፍ እነሱ እንደሚሉት የጀመሩትን የልማት ዕቅድ ለመተግበር ሳይሆን ኢትዮጵያን የማፈራረስና ኢትዮጵያውነትን የመጥፋት ዘመቻቸውን ለማስቀጠል የሚያረዳቸውን ማንኛውንም እርምጃ ሁሉ ከመውሰድ ወደ ኋላ አንደማይሉ የተረጋገጠ ነው::

እንደ እኔ አስተሳሰብ የወያኔ ኢሕአዲግ መንግስት በምንም ታአምር በምርጫ ተሸንፉ ስልጣኑን በቀላሉ ይለቃል ወይም ስልጣኑን ለተቃዋሚዎች ያጋራል የሚል እምነቱም የለኝም::በአሁኑ ሰአት እንደምናየው እንዲሁ በቀላሉ የኢሕአዲግ መንግስት ስልጣኑን ይለቃል ወይም ለተቃዋሚዎች ያጋራል ብሎ ማሰብ የዋህነትና የማይታሰብ ጉዳይ ቢሆንም ነገር ግን ወያኔና የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆድና ጀርባ እንደሆኑ ለብዙ ጊዜ እንደማይቀጥል በምሪት እና በህልእ የተሞላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጣ ገንፍሎ ወያኔ ዳግም እንዳያንሰራራ ወደ መቃብር ይወስደዋል ብዬ አምናለው:: ስለዚህ የወያኔ መሰሪ አካሂድ ተስፋ ሳያስቆርጠን የወያኔን መንግስት በተገኛው መንገድ ሁሉ በመታገል እና በመቃወም የኢትዮጵያን ሕዝብ ነጻነት ለማረጋገጥ ትግላችንን ማቀጣጣል ይጠበቅብናል::ኢትዮጵያ በቆራጥ ታጋይ ልጆቿ ከወያኔ አገዛዝ ነጻ ትወጣለች::

ድል ለሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

gezapower@gmail.com
Image
gezahegn abebe.jpg

ያረጋገጥነው የምግብ ኢ_ዋስትናን (ዋስትና አላልኩም) ነው –ክፍል 5 [የመጨረሻው ክፍል]

0
0

ሠሎሞን ታምሩ ዓየለ

ይህንን ክፍል ስጀምር አንባቢያንን እንዲህ በማለት ነው። በሕዝቦቿም ሆነ በዓለም አቀፍ መድረክ ሥራቸውና መልካም ተግባራቸው የተመሰገነላቸው፤ የተወደሰላቸው፤ የተጨበጨበላቸውና ውዳሴ የተቸራቸውን ድንቅዬዎቹን ኢትዮጵያውያን ሁሉንም ባይሆን ጥቂቶቹን ለሰከንድ በኅሊናችን እንድናስባቸው በመጠየቅ ነው። እነርሱ ለኛ ሻማ ናቸው። እራሳቸውን በጥረታቸው አብርተው ብርሃኑን ለኛም እንዲደርሰንና እንድንገለገልበት መንገዱን መርተውናል። እኛ ግን እርኩስና ስንኩል መንገድ ይሻላል ብለን የራሳችንን ፍልስፍናና የኑሮ ዘይቤ ትተን የሌሎቹን የማናውቀውንና ለኛ ኅ/ሰብ ምቹ ይሁን አይሁን በቅጡ ሳናረጋግጥ የተበላሸና የማይሰራ መንገድ መርጠን እነሆ ስንገታገት ግማሽ ምዕት ዓመት ሊሞላን አንድ አሥር ዓመት ቀረን። አንዳንዶቻችን የአዳምና የሔዋን ልጆች መሆናችንን እረስተን በማንነት ዙሪያ ብቻ ስናወራ ጊዜው በረረ። ሐረር የኖራችሁ ታውቁታላችሁ ብዬ አስባለሁ። ይህ ሰው የ፫ተኛው ክፍለ ጦር ኦጋዴን አንበሳ የሙዚቀኛው ክፍል (የቀላድ አምባው) ድምጻዊ ነው። መስፍን ከበደ ይባላል ። ሹመቱን እረሳሁኝ። ወታደር ሲኖርም፤ ሲሞትም በማዕረግ ስሙ ነው የሚጠራው። አስቀድሞ ታይቶት ነው መሰለኝ በ1960ዎቹ አጋማሽ እንዲህ በማለት አቀንቅኖ ነበር፦ ትውልዳችን የዓዳም አንድ ነው ደማችን፤ ከቶ ለምን ይሆን ዘር መለየታችን? ለውጥ በኑሮአችንና በአስተሳሰባችን ሲያልፍም አልነካን። በጊዜ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ከፋም ለማም በሆነ ነገራቸው ለውጥ መታየት ነበረበት። በምሳሌም እንደተማርነው ” ምንም ያህል ዘመን በውሃ ውስጥ ቢኖር መዋኘት የማይማረው ድንጋይ ብቻ ነው” ተብሎ በተለይ የምዕራብ አፍሪካ ሰዎች ነገር በምሳሌ እንዳላቸው አንድ ወቅት ላይ ከረፖርተር ጋዜጣ ላይ ያነበብኩኝ መሰለኝ። ለማለት የፈለኩት እኛም በቂ እንዳልተማርንና ስህተትን በሌላ ስህተት ከመተካት በስተቀር ትርፍ ያመጣና ሕይወታችንን ከጎስቋላው ኑሮ ፈቀቅ ያደረግ እርምጃና ለውጥ አለማየታችንን ለመናገር ፈልጌ ነው።
Food security ethiopia
ለዘመናትና ዛሬ ድረስ የኢትዮጵያ ገበሬ የተለያዩ የዕጽዋት ዝርያዎችን በመስኩ ላይና በጎተራው በመንከባከብና በመጠበቅ የሰው ልጅ ህልውና ታሪክ ከምድረ ገጽ እንዳይጠፋና እንዲቀጥል የበኩሉን ድርሻ እንደ አቅሚቲ ተወጥቷል። ለዓለምም ሕዝብ እንደ ቡና፤ እንሰት፤ ኑግ፤ ኮረሪማና ሌሎች ቅመማ ቅመሞችን፤ ኦክራ (የሴት ጣት)፤ ጤፍ፤ የተለያዩ የገብስ ሰብል ዓይነቴዎችን፤ ባህላዊ መድሃኒት የሆኑትን የኮሶና የድንገተኛ ዕጽዋቶችንና ሌሎች ሰብሎችንና እንስሳቶችን ጠብቆና በእንክብካቤ አቆይቶ ፤ ለራሱ ሳያልፍለት ለሌሎች አቀብሎና ሰጥቶ ቆይቷል። መልሶም የእነርሱ ተረጂም ሆኗል። ለዚህ ሁሉ ተግባሩ ደግሞ የአገሬ ገበሬን ዕውቅና ቢቸረው ቢያንስበት እንጂ አይበዛበትም። ለምሳሌም ያህል ለመጥቀስ የአሜሪካን የገብስ ሰብል ገበሬዎች ይህንን ውለታውን ጠንቅቀው ያውቁታል። ለምን ይህ ሁሉ የሰው ሃብትና እምቅ የተፈጥሮ ሃብቶች ኖሮን እንዲህ ምድር ለኛ ብቻ ሲዖል የሆነችብን ብለን መጠየቅም ተገቢ ነው። ይህንንም ገጥታችንን ለመቀየር መፍትሄው እኛ ዘንድ እንጂ ሌላ ስፍራ እንደማይኖር ተገንዝበን ቀናውን መንገድ መከተል የሁላችንም ኃላፊነት ነው ብለን መነሳት እንዳለብን ለመጠቆምም ነው።
ግብርና የአገራችን ዋነኞ ኢኮኖሚ መሰረት ነው። ለዕድገታችንም መሰረቱ ግብርናው ነው ካልን አገራችን የገበሬ ምድር ናት ማለት ነው። አዎን! አገራችን ኢትዮጵያ፦ የአፈር ገፊው፤ የእንስሳት አርቢው፤ የዓሳ አስጋሪው፤ የደንና ዱር አራዊት ጠባቂው፤ የንብ አናቢውና የማር ቆራጩና የሌላም ልጆች አገር ነች። ለምን ቢባል በክፍል 4 መጨረሻ ላይ ጠቀሜታው ተገልጾአል። ግብርና ክቡር ሙያ ነው። ገበሬም እንደዚያው ማለፊያና ደግ ነው ። የአገራችን ኢኮኖሚ ምን ያህል ከግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ጋር የተቆራኘ ለመሆኑ ተደጋገመው የሚነገሩትን አኅዛዊ መረጃዎች መመልከቱ ይበቃል። እጅግ በድህነት አረንቋ ውስጥ ለሚገኘው 80% በላይ ለሆነው የአገራችን ሕዝብ ለኑሮው መሰረቱና መደበኛ ሥራው ነው። ከጠቅላላው የአገሪቱ ምርትም ውስጥ ድርሻው 50 % ነው። የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት ወደ ዓለም ገበያ ከሚጓዙት ሸቀጦቻችንም እስከ 85% ድርሻ አለው። ዋነኛ የኤክስፖርት ምርታችን ብለን የምንጠራው የኮኖሚው ዋልታ ቡና ቡና 25% ድርሻ አለው። በተጨማሪም የእንስሳት ሃብታችንም ቢሆን ለብቻው ከጠቅላላው የግብርናው ምርት ውስጥ 15% ስፍራን ይይዛል።

የአገራችን ግብርና ዋና ዋና ገጽታዎቹ ምንድር ናቸው? በዋናነት የሰብል ልማት ላይ ያተኮረው ግብርናችን የዝናብ ጥገኛ ነው። የዝናቡ ተስተካክሎ በጊዜው መምጣት፤ መጠኑና ሥርጭቱ ለምርቱ ብዛትም ሆና ጥራት ወሳኝ ናቸው። የምግብ እህሎች የሚባሉቱ የብርዕና የአገዳ (ጤፍ በቆሎ ማሽላ ስንዴ ገብስ አጃ ዳጉሳ) ፤ ጥራጥሬ (ባቄላ አተር ምስር ሽምብራ አኩሪ አተር አደንጓሬና ሌሎች)ና የቅባት (ኑግ ሰሊጥ ተልባ ለውዝ) እህሎች በዋነኛነት የለማውን ማሳ (ከ80 _90%) እጅ ሸፍነውት ይገኛሉ። እንደ ጠቅላይ ስታትስቲክስ ጽ/ቤት የ2005 የግብርና እንቅስቃሴ ናሙና ጥናት ረፖርት መሰረት ( አሃዙን ለማንበብ እንዲመች ወደ ሚቀርበው ለማጠጋጋት ተሞክሯል) በምግብ ሰብል ምርት የተሸፈነው ማሳ በጠቅላላው (በአነስተኛና በዘመኑት እርሻዎች በመኽርና በበልግ ወራት) መጠን 12 1/4 ሚሊዮን ሄክታር ሲደርስ ከእዚሁ ማሳ ላይ ብቻ ወደ 231 ¼ ሚሊዮን ኩንታል የሚደርስ እህል እንደተሰበሰበ ተገልጾአል ። እስቲ ስለዚህች አሃዛዊ መረጃ መሰረት አድርጉና ለጠቅላላው ሕዝብ ቁጥር ግምት አካፍሉትና የሚሰጣችሁን የነፍስ ወከፍ ዋጋ ተመልከቱት። ምን ይሰማችኋል? ይሄ የነፍስ ወከፍ ዋጋ የአትክልትና ፍራፍሬ፤ የሥራ ሥሩንና የቅመማ ቅመሙንና ሌሎችን ውጤት እኮ አይጨምርም። ታዲያ ውጤቱ ትክክል ነው ብለን የምናምን ከሆነ፤ ለምን በረሃብ ፤ በችጋርና በጠኔ እንሰቃያለን? ግብርናችን አንድ ቦታ ላይ በችግር ተውተውትቧል ማለት ነው። በተደጋጋሚ ለእርሻ አገልግሎት የዋሉት ማሳዎች የለምነት ደረጃቸው የቀነሰ ነው። አስተራረሳችን በአብዛኛው እጅ ዛሬም ጥንታዊና በዘልማድ ላይ የተመሰረት ነው። በኢትዮጵያ ምድርና ማሳዎች ላይ ብዙ ትራክተሮችና ተጎትተው የሚሽከረከሩ መሳሪያዎች አያጔሩም፤ የማጨዳ መውቂያና መፈለፈያ መኪኖች አይሽከረከሩባትም። በአገሪቱ አገልግሎት ላይ የትራክተሮች ብዛት ለሚታረሰው መሬት ወይም ደግም ለገበሬው ቁጥር ቢካፈል ድርሻው በጣም አነስተኛና ደካማ ነው። ይህም ማለት ግብርናችን በአብዛኛው በእጅ ሃይል የሚከናወን ነው ማለት ነው። የምርት ማሳደጊያዎች አጠቃቀማችን እንዲሆን ከምንፈልገው እጅግ ወደ ታች የተጎተተና የራቀ ነው ። በአትክልትና ፍራፍሬ፤ የሥራ ሥር ተክሎች የተሸፈነው ማሳም ስፋት ትልቅ ነው። የኢኮኖሚ ዋልታ ቡናችንም ለብቻው የያዘው የማሳ ስፋት ክ1/2 ሚሊዮን ሄክታር በላይነው። የጫት ተክሉም ቢሆን ቀላል ግምት የሚሰጠው አልሆነም ። ከፍተኛ የሰው ኃይል የተሰማራበት ይህ የሰብል ልማት ንኡስ ክፍል ምርትና ምርታማነቱ እጅግ በአነስተኛ ደረጃ ለይ ነው። ለምርትና ለምርታማነቱ መጨመር ተገቢው ስፍራ የተሰጣችው የግብአት ( ምርጥ ዘር፤ የመሬት ማዳበሪያ ፤ ጸረ_ተባይና ሌሎች) አጠቃቀሙ በዝቅተኛ ደረጃ ለይ ነው በተለይ በግብርናቸው ዕድገት ላይ የጎላ ለውጥ ካስመዘገቡት አገሮች ተርታ ሲነጻጸር። ዛሬም ብሐራዊ የበቆሎ ምርት አማካዪ ከ25 _30 ኩንታል/ ሄክታር በላይ አልዘለለም። በምርምር ጣቢያዎች፤ በአንዳንድ ሠፋፊ እርሻዎችና በጣት የሚቆጠሩ የገበሬዎች ማሳ ምርቱ ከፍ ያለ እንደሆን ይነገራል። የምንኮራበት የጤፍ ሰብልም በአስራዎቹ የመጀመሪያ ረድፈ እንጂ ከአስራዎች ግማሽ በላይ አልወጣም፤ ማሽላም ከ20 ኩንታል/ ሄክታር በላይ አልዘለለም፤ የባሌና አርሲ የስንዴ ሰብል ቀበቶዎች ብለን የምንጠራችው ስፍራዎችም የሚመዘገበው አማካይ ምርት ከሄክታር ከ20 ኩንታል በቅጡ አልተሻገረም። ይህ ማለት ደግሞ ከዚህ በላይ መጓዝ አይችሉም ማለት እንዳልሆነ አንባቢ ግንዛቤ እንዲያገኙ ይጠየቃሉ። ባጭሩ ሁኔታዎቹ ተሰፋ አስቆራጭ ናቸው ማለት አይደለም። በተቃራኒው መቆም የሚያስችል ችሎታ በገበሬውም በተፈጥሮም አሉ። ዋነኛ የግብርናው ተዋንያኖቹ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው ከእጅ ወደ አፍ የሚያመርቱ በመጨረሻው የድህነት መስመር ላይ የተሰለፉ ግፉአን አምራቾች ናቸው። የይዞታ መጠናቸውም ከድሮው እጅግ በፍጥነት እያሽቆለቆለ መጥቶ ከ 1 ሄክታር በታች መሆኑ ከተገለጸ ሰነባበተ። ቁጥራቸው በዛ ያለ ገበሬዎችም ከኩርማንና ከበሬ ግንባር ያላነሰ መሬት መጠን ይዘው ይማስናሉ። መቼስ የአባ ወራው ሆነ የእማ ወራው ብዛት ስንት እንደሆን በቅጡ አይታወቅም። ከጠቅላዩ ስታትስቲክስ የተለቀቁት መረጃዎች እንደሚጠቁሙትና እነሱንም መሰረት በማድረግ የቤተሰቡን ቁጥር ሳይጨምር ከ14 ሚሊዮን በላይ ሳይገመት አይቀርም። ከእዚህ ውስጥ ምን ያህሉ ወንድ ?ምን ያህሉ ሰቶች? እንደሆኑ የሚታወቅ አይመስልም። በእድሜ ደረጃም ቢሆን፤ በመደበኛ የትምህርት ችሎታቸው ተለይቶ የተቀመጠ መረጃ ለማግኘት ያስቸግራል። ሌላም ልጨምር በየተሰማራበት ንዑስ የሥራ ክፍልም ምን ያህል እጁ እንደሆነ የሚገልጥ ቀጥተኛ መረጃ በቀላሉ ማግኝት አይቻልም። ይሄን ጊዜና ነው የጠቅላይ ስታትስቲክስ መ/ቤት እጅግ አስፈላጊነትና መልካም መግለጫ ሰጭነት ስፍራው። ” ሃሎ ሃሎ ሃሎ ሃሎ ጠቅላይ ቢሮ “ በ1950ዎቹ የተጫወተው ባህታ ገ/ሕይወትም አይደል። መረጃ ዘርዘርና ረቀቅ ተደርጎ ሲቀርብ ለሚተነትነው አካልም ሆነ መረጃውን መሰረት አድርጎ አገልግሎቱን አዘጋጅቶ ለተጠቃሚው በበቂ ለማድረስ ደፋ ቀና ለሚሉት ተቋሞችና ድርጅቶች እጅግ ይጠቅማል፤ ያግዛልም፤ ይረዳልም። ይህ ስራው ሁሉ ከእጅ ወደ አፍ ብቻ የሆነው ገበሬ ለዕለት ተዕለት ለቤተሰቡና ለራሱ ምግብ ፍጆታ የሚውል ምግብ እንጂ የሚያመርተው እንዲህ ተርፎት የከተማውን ነዋሪ ለማጥገብ ተገቢውን ድጋፍ ከሚመለከታቸው ካልተቸረው በስተቀር የዳገትን ያህል አስቸጋሪ ነው። እንግዲህ ሰለ ግብርናው ልማትና ዕድገት ሰናወራና መግለጫ ስንሰጥ በቅድሚያ ስለሱ መሆን አለበት። ችሎታውን ሳንንቅ፤ አቅሙንና ክህሎቱን ሳንለካ ብዙ ጊዜ አላዋቂነቱን እንሰብካለን። ገበሬ አካባቢውን ጠንቅቆ ያውቀዋል። ጥሩ ተመራማሪ ነው። የተመራማሪው ሳይንቲስት ሥራ መሪውና መምህሩ ገበሬ ነው። ከእርሱ ችግሮቹን ጠይቆና ለይቶ ቅደም ተከተል አስይዞም አይደል ፤ ለችግሮቹ መፍትሄ ለማበጀት ምርምሩን በመስክና በቤተ ሙከራ የሚያደርገው። እኛ እናውቅልሃለን የምንለው የምንበልጠው ችሎታችንን በወረቀት ላይ ባማስፈርና ሰነዶችን በማዘጋጀት፤ ለስብሰባ ብቁ እንዲሆኑ በማቅረብ ነው ብል ብዙ ስህተት ላይ አልወድቅም። ታዲያ ሁላችንም ብንሆን ለሃገሪኛው ዕውቀትና ክህሎት ተገቢውን ስፍራ ብንሰጥ ማለፊያ ስራ ነው ለማለት ይቻላል። በተጨማሪም እኒሁ ገበሬዎች እንደ መንግስት ሹመኞች፤ የፖለቲካ አዋቂዎችና ሌሎች አካላቶች ሁሉ ሰዎች መሆናቸውን አንዘንጋ። በቂ ችሎታና ክህሎት ያላቸውና ሥራን እንደ አቅሚቲ በመፍጠር ኑሯቸውን ለማሸነፍና ለማሻሻል የሚፍጨረጨሩና እምቅ ሃይልና በተስፋ የሚኖሪ፤ ከዛሬ ነገ ይሻላል ብለው የሚጓዙ መሆናቸውንም ከግምት ውስጥ እናስገባ። የዚህን ሰብል አብቃይ አነስተኛ ይዞታ ለይ የሚገኙትን ገበሬዎች በመርዳትና በማገዝ በብዛትና በዓይነት ምርት አምርቶ ወደ ገበያ በማውጣትም ለኑሯቸው በቂና አስተማማኝ ገቢ አግኝተው ወደ ተሻለ የኑሮ ደረጃ የሚረማመዱበትን መንገድ አቅጣጫ ማስያዝ አጣዳፊ ተግባር ነው። ይህንን ስንፈጽም ብቻ ሰለ ምርትና ምርታማነት ከፍ ሲልም ስለ ምግብ ዋስትና ማረጋገጥ የምናወራው።

ከእንሰሳት ሃብታችንም የምናገኘው ጥቅም በበቂ አገልግሎ ት ላይ የተመሰረተ ነው ብሎ አፍን ሞልቶ ለመናገር ያስቸግር ይሆናል። ቢሆንም ይኽው ሃብታችንን እንዳያድግ ቀፍድዶ የያዘንን ችግሮች ለይተን አውቀን ቅደም ተከተል አስይዘን ተገቢውን ድጋፍና እገዛ ለአርቢዎቻችን ካደረግን ተጠቃሚ የማንሆንበት ምክንያት የለም። ከጠቅላይ ስታትስቲክስ ቢሮ የተለቀቀ የቅርብ ጊዜ መረጃ እንደሚያመለክተው (2005 እ ኢ አ) አገራችን ወደ 50 ሚሊዮን የሚደርሰ የከብቶች፤ ከ20 ሚሊዮን በላይ የበጎች፤ ወደ 20 ሚሊዮን የሚጠጉ ፍየሎች፤ ወደ 45 ሚሊዮን የሚጠጉ ዶሮዎችና 2 ሚሊዮን ተግማሽ የሚደርስ የንብ ቀፎ የተሰማራባት በለሃብት ነች። ፈረስ፤ አህያ፤ በቅሎንና ግመልን መረጃው ስላላስፈለገኝ አልጠቀስኩትም። ይኽው ዋነኛ የአገራችን የመረጃ ምንጭም ጽ/ቤት ከላይ በተጠቀሰው ዓመት ብቻ የዘመናዊውን የእንሰሳት እርሻዎች ምርት ሳይጨምር ወደ 3 1/3 ቢሊዮ ን ሊትር ወተት፤ 176 ½ ሚሊዮን ሊትር ጥቂት ፈሪ የግመል ወተት፤ ወደ 40 ሚሊዮ ን ኪሎ ግራም የማር ምርት፤ ወደ 94 ½ ሚሊዮን በቁጥር የዕንቁላል ምርት (ትንሽ ነው፤አንድ ዕንቁላል ለአንድ ሰው እንደማለት ነው። አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ከዕንቁላል በሚገኘው ፕሮቲን ዕጥረት ይሰቃያል ማለት ነው።) ከአነስተኛ ይዞታ ካላቸው አርቢዎች አገሪቷ እንደሰበሰበች ገልጿል። የነፍስ ወከፍ ድርሻችንን ለማወቅ ያው እንደተለመደው ማካፈል ነው ለሕዝብ ቁጥር። ትክክለኛ ቁጥር ከሆነ ይናገራል፤ ይገልጻል፤ ዓይን ይከፍታል። የውሸት ከሆነ ደግሞ አይታይም፤ ምኞት ነው። ስለሆነም ኩነቶችን በአግባቡ አይገልጥም፤ አያስረዳምም። ጉም ነው። ጥጥ ነው። ብን ብሎ ይጠፋል።

በዋናነት የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ በፍጥነት ለማሳደግ የሚረዳው መንገድ የገበያና የኢንዲስትሪ መሰረትን ሊያስጥል የሚያስችለን በዘመናዊ ዘዴ እርሻ የሚያርሱና የሚያበቅሉ እንዲሁም እንስሳትን የሚያረቡና ተዋጽዖዎችን በብዛትና በጥራት ለተጠቃሚው በተመጣጣኝ የገበያ ዋጋ የሚያከፋፍሉ እርሻዎችን ማስፋፋትና ቁጥራቸውንም በየጊዜው እንዲጨምሩ በማድረግ ነው። እነዚህኑ ገበያ መርና የዘመኑትን እርሻዎች ማብዛትና ማስፋፋት በአነስተኛ ይዞታ ላይ የሚገኙትን ሰብል አብቃዮችን ሆነ እንስሳት አርቢዎችን እንዲሁም ንብ አናቢዎችንና ዓሳ አስጋሪዎችን ጨምሮ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ፤ በጠቃሚም ሆነ በጎጂ ጎኖች እየታየና ውጤቱም በአግባቡ እየተገመገመ በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ለውጥና ግፊት እንዲያመጣ ዝግጅቱን ከወዲሁ ማጠናቀቁ ይጠቅማል እንጂ አይጎዳም። እነዚህ ሰፋፊ እርሻዎችን ዓይነትና የይዞታ መጠናቸውን ለመግለጽ የተደራጀ መረጃ ማግኘት አስቸጋሪ ነው። ብዙም ሰለነሱ ማውራትም ያዳግታል። ምን አልባትም ከመንግስት የመሬት መቀራመት ዝብርቅርቅ አሰራር ጋር ያስከተለውን ችግር ተመልክቶም ሊሆን ይቻላል።

ለመሆኑ ከእዚህ አስፈላጊና መሰረታዊ ብለን ከጠራነው ክፍለ ኢኮኖሚ ጀርባ የትኞቹ ተቋሞች ናቸው የሚገኙት? በእኔ ዕይታ በዋናነት ብዬ ከምጠቅሳቸው ልጀምር።

ፓርላማ (ምክር ቤት)

የአገሪቱ የምትደዳርበትን ሕግ፤ ደንብ፤ ሥርዓትን ከሚቀርጸውና ከሚያጸድቀው የሕዝብ ተወካዮችና የፌደራል ምክር ቤት ብንጀምርስ? ይህ በሕዝብ ድምጽ የበላይነት አግኝቻለሁ ብሎ በየአዳራሹ ሰብሰባ በማድረግ የሚያስተላልፈው ውሳኔ መንግስት የሚባለውን ተቋም ፍላጎት ወይስ የአርሶ አደሩን ጥቅም አስጠባቂ ነው? የሕዝብ መሰረታዊውን ፍላጎት ተመልክቶና ተከታትሎ ነውን የተጣለበትን ኅላፊነት የሚወጣውን? ለመሆኑ ስለ አገሪቱ ግብርና ይዞታ በየዓመቱ ስንት ጊዜ እንደ ዋነኛ አጀንዳ ቆጥሮ ተወያይቶበታል? ምንስ ያህል ጠቃሚ ውሳኔዎችን አሳልፏል? በመገናኛ ብዙሃን ዜና እንደምንሰማው የም/ቤቱ አባላት ጎበኙ፤ አደነቁ፤ የሚኒስቴሮችን ረፖርትአዳመጡና ማብራሪያ ሃሳብ ጠየቁ? በቃ ይሄው ነው እርምጃችሁ? አለቀ ደቀቀ! ሕዝብ ስራችሁን የሚገመግመው መንግስት ለማድረግ የፈለገውን በመደገፍ ብቻና በምታወጡት እጅ እንዳልሆነ ስንቶቻችሁ ታውቁት ይሆን? ከተከበሩት የፓርላማው ተወካዮች ተነሳሽነት አሳይተው ከላይ ለጠየቅሁት ጥያቄ ተገቢ መልስ የሚሰጥ ይኖር ይሆን ?

ግብርና ሚኒስቴርና የክልል ግብርና ቢሮዎች

እንደ አውሮፓዊያኑ የዘመን ቀመር በንጉሥ ምንይልክ አስተዳደር ዘመን በአዋጅ በ1907 ዓም የተቋቋመው የአሁኑ ግብርናና የገጠር ልማት ሚኒስቴር ቀደም ሲል ጀምሮ ለበርካታ ጊዜያት ስሙንም ቀያይሯል። ለመጥቅስም ፦ የእርሻ፤ የእርሻና ሕዝብ ማስፈር፤ የእርሻና የመሬት ይዞታ፤ የእርሻ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት፤ የግብርናና የአካባቢ ጥበቃ ስሞቹ ለአብነት ከሚጠቀሱቱ ዋነኞቹ ናቸው። ቁም ነገሩ ከስሙ ምን አለን ነው የሚባለው። ከፊታውራሪ፤ብላቴና ደጃዝማች ማዕረጎችን ጨምሮ በትምህርታቸው የዶክተር ማዕረግ ያላቸውንና በዕውቀታቸው በልምዳችው፤ በክህሎ ታቸውና በአስተዳደር ችሎታቸው የተከበሩና የተመሰገኑ ትጉህ የሆኑት ጨምሮ የወያኔ/ ኢሕአደግ የጦር አበጋዝ የነበሩት አቶ አዲሱ ለገሠን በሚንስትር ማዕረግ መርተውታል። አንዳንዶቿም ለሁለተኛ ጊዜ በድጋሚ ተሹማዋል። ለመጥቀስም፦ ዶ/ር ገረመው ደበሌና አቶ ዘገዬ አስፋው ናቸው። ፎቷቸውም በካዛንቺስ በሚገኘው የሚኒስቴሪ ጽ/ ቤት መግቢያ አዳራሽ ተስቅሏል። ጠቅላላ ቁጥራቸውን ለማወቅ ከጽ/ ቤቱ ማግኘት ይቻላል። አንዳቸውም ግን የአገሪቱን ግብርና ኢኮኖሚ ከፍ አድርገው ጥግ አልያሲያዙትም ወይም አላነሱትም። ነገር ግን በቀድሞዎቹ ሚንስትሮች ጊዜ አገሪቷ እንዲህ እንዳሁኑ የችጋር፤ የረሃብን የድርቅ ምሳሌ ሆናና ለዜጎቻ ማፈሪያ የሆነችበት ጊዜ ከ1966 ዓም ድርቅ በስተቀር የከፋ ጊዜ በታሪኳ አታውቅም። አንድ የጋራ የሆነ ጠባያቸው አላቸው። ይኽውም የኢትዮጵያ ሕዝብ ለጥረታቸው አድናቆትን አልቻራቸውም፤ አላጨበጨበላቸውም፤ ዘፈንም ሆነ ግጥም አልዘፈነምም፤ አልገጠምምም። እኔ የማስታውሰው የዶ/ር ገረመውን መንበር በ1975 ዓም የተረከቡት አቶ ተኮላ ደጀኔ ግን በወሰዱት የፈጣን የመዋቅር ማሻሻያና ማስተካከያ እርምጃ በዋናውና በየክፍለ ሃገሩ ዋና ከተሞ ች ለይ ብቻ ተኮልኩሎ የተቀመጠውን የሰው ሃይል ገበሬውን ተጠግቶ አገልግሎቱን እንዲቸረው በማሰብ በተወሰደው እርምጃ ሰለባ የሆኑቱ እንዲህ ባማለት ተቀኝተው ነበር። በተኮላ፤ ጉዴ ፈላ።

በመሠረቱ ይህ የሚኒስቴር መ/ቤት ሲዋቀር በዋናነት ኃላፊነት የተሰጠው የአገሪቱን ግብርና ልማት ለማስፋፋትና ለማሳደግ ሲሆን በተጨማሪም የተገቢ ፖሊሲ ሃሳብ በማመንጨትና ለተግባራዊነቱም አርሶ አደሩን ማዕከል በማድረግ የአኗኗር ዘይቤውን ደረጃ በደረጃ ለመለወጥ ነበር። ግብርና ሚኒስቴር እኔ እስከማውቅው ድረስ የሰራው መዋቅር እራሱኑ መልሶ አላሰራው እያለ ማነቆ ስለሆነበት እንዲሁ ራሱን በማዋቀር ጥሩ የሥራ ጊዜውን ያጠፋ መ/ ቤት ነው። ዋናው ግብርናን ተልዕኮ የሚያስፈጽመው ክፍል ተገፍቶ ድጋፍ ሰጪና የአስተዳደርና የፋይናንስ ክፍሉ አንበሳ የሚሆኑበት ጊዜ ይበዛል። መዋቅሩ በቀላሉ ስራን በመደገፍ የሚያቀላጥፍ ሳይሆን ትከሻቸውንና ኃያልነታቸውን ለማሳየት ብቻ በሚሞክሩ አለቃዎች ተሞልቷል። መዋቅሩም ቢሆን ግዙፍና ቦርቃቄ ፤ በእዝ ሰንሰለት የተንዛዛ ነው። ዛሬ ደግሞ ይህ መዋቅር በክልል፤ በዞንና እስከ ወረዳና ቀበሌ ድረስ የተዋቀረ ነው። ጥያቄው ለምን ተዋቀረ ሳይሆን ተልዕኮውን የአቅሙን ያህል ድርሻውን ይወጣል ነው። አንድ የጥበብ ሰው ሠዓሊን ግብርና ሚ/ርን ሳለው ተብሎ ሥራ ቢሰጠው በብሩሹ እጅግ ግብዳ፤ ግዙፍና ቅርጽ የሌለው ሰው አድርጎ ሰርቶ ያስቃችኋል። ግብርና ሚ/ ር በተማረ የሰው ኃይልም ቢሆን ከትምህርት ሚኒስቴር ቢበልጥ እንጂ አያንስም። ምሁራኖቹን በአግባቡ የተጠቀማባቸውና በችሎታቸው ያሰማራቸው አይመስልም። የግብርና ሚ/ር ካለው ነገር ሁሉ የዘመቻ ስራ ይወዳል። ደራሲ በዐሉ ግርማ በኦሮማይ መጽሃፉ እንደጠቀሰው ለቀይ ሽብር ዘመቻ፤ ለአረንጓዴው ዘመቻ፤ መሃይምነትን ለማጥፋት ዘመቻ፤ የቀይ ኮከብ ጥሪ ዘመቻና ሌሎችም ማለቂያ የሌላቸው ዘመቻዎች አይነት እኔ በማውቀው ግብርና በሽ ነበር። ዛሬም ቢሆን ይህ በሽታ ጠፍቷል ከነጭርሱ ብሎ ለመናገር አይቻልም። የዘመቻ ሥራ የአንዴ ተግባር ስትሆን ተሰተካክላ በሯሷ አትቆምም፤ አትቀጥልምም። ምንአልባት የዘመቻ ሥራ ለሃገር መካላከያ ሠራዊት በፍጥነት ጠላት ሳይደራጅበትና መሬት ሳይዝበት ሊጠቅመው ይችላል። ለሁሉ ነገር ግን ዘመቻን እንደ ዋነኛ የስራ ስልት አድርጎ መቀጠል ሥራን ያበላሻል። የሕግ አስፈጻሚነት ድርሻውን ከኤክስቴንሻ ን አገልግሎቱ መለየት መቻል አለበት። የሚያወጣቸው መረጃዎቹና የሰብል ግምገማ ረፖርቶቹ መሆን ያለባቸው በተጨባጭ በተሰበሰቡና እውነትነት ኖሯቸው በሚያሳምኑና ምክንያት ባላቸው ላይ ተመስርተው እንጂ የባለሙያውን ግምት፤ፍላጎትና ዕውቀት ብቻ መሰረት አድርገው መሆን የለባቸውም። ጥሩ ምርታማነት በተወሰኑ በጣት የሚቆጠሩ አርሶ አደሮችን ውጤት ብቻ እያጎላን ስለ ተቀረው ገበሬ ጭምር አድርገን የምናወራና ረፖርት የምናደርግ ከሆነ እየሰራን ሳይሆን ምኞታችንን እያጋነንን ነው የምንገልጸው። በተጨማሪም ነፍሳችንን ነው ደስ ያሰኘናት እንጅ በተጨባጭ ያረገገጥነው የለም። ዛሬም ቢሆን የኢትዮጵያ ገበሬ ምርታማነት በዓለም በሚገኙት ገበሬዎች ሁሉ በአብዛኛው ምርቶቹ በዝቅተኛ ደረጃ ለይ ነው። በ1980ዎቹ መጨረሻና 1990ዎቹን ይዞ በዘመቻ መልክ የተጀመረው “ኤክስቴንሺን ፓኬጅም” በአንዳንድ ስፍራዎች ምርትና ምርታማነተን ቢያጎናጽፍም በሌሎች አስፈላጊ ተብለው በተጠቀሱ ስልቶች ስላልታገዘ የተፈለገውን ውጤት ያመጣ አይመስልም። “የኤክስቴንሺን ፓኬጁም” በአንዳንድ ክልሎች፤ ዞኖች፤ ወረዳዎችና በተለያዩ ልማት ጣቢያዎች የፉክክርና የመበላለጥ ስሜት የነገሰበት አሰራር እንዲነግስ መንገድ በመክፈቱ ስራዎቹን ለመከታተል የልማት ሰራተኞቹ በውጥረት እንዲሰሩ አስገድዷቸው እንደነበር በገሃድ የታየ ሃቅ ነበር። እንደ ኢትዮጵያ ሬዲዮ የአንድ ሰሞን የዜና ዘገባ መሰረት ክልሎችም ሆኑ ወረዳዎች ጤናማና አካባቢን ያላገናዘበ ውድድር ውስጥ የገቡ ይመስል ይሄን ያህል ገበሬዎች በዚህ ፓኬጅ ታቀፉ፤ ይሄን ያህል መሬት በዚህ ሰብል ተሸፈን፤ ይሄን ዓይነት ግብዓት በዚህ መጠን ለገበሬው ተሰራጨ፤ ይሄን ያህል ምርት ተሰብሰቦ ይሄን ያህል የሚገመት ብር ገበሬው አገኘ፤ የገበሬው ምርታማነት ጨመረ የሚል የተጋነነ ወሬ መልቀቅ ስራዬ ተብሎ ተይዞም ነበር። አንዳንዴም ታረሰ የሚሉትና ተገኘ ብለው የሚዘግቡት ደግሞ ከሰብሉ የዘር መጠን በብዙ የዘለለ አይመስልም ( አጃይባ ነው)። እነዚህ የተጋነኑና እጅግ ጥቂት ገበሬዎችን የሚገልጹ ረፖርቶች ከፕሮፓጋንዳ ከመንዛት የዘለለ ለድሃው አርሶ አደር አስገኝተውለታል ተብሎ የሚነገር የኑሮ ለውጥም፤ ሸማቹንም ህብረተሰብ ጨምሮ ካለምንም ማጋነን የለም። ይህንንም ስል ስራዎቹ አልተሰሩም፤ አልተለፋም፤ አልተደከመም፤ አልተወጣምና አልተወረደም ለማለትና ለማጣጣል ፈልጌ አይደለም። ስንቱ በየክልሉ፤ በዞን፤ በየወረዳውና በየልማት ጣቢያው የሚገኝ የልማትም ሆነ ከስራው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የሌላችው ሁሉ ባጭር ጊዜ የመስክ ስልጠና በዘመቻው ላይ ተሳትፈዋል። ይህንንም በዓይኔ በብረቱ ያየሁት ነው። ችግሩ ግን ጋዜጠኞች ተብዬዎቹ ስራውን በአፋቸው ላይ በፕሮፓጋንዳ ጨረሱት። የበረከተውና የተለቀቀው ” የዜና ምርት “ እንጂ የእህል ምርት ሆኖ አልተገኘም። በቁጥርና በአኅዝ የገበሬውን ቤት ምርት በምርት አደረጉት። ይገኛል ተብሎ ተገምቶ የተሰጣቸውን ምርት በመሰላቸው ዋጋ እያባዙ ጭቁኑን ገበሬ ብር በብር አደረጉት። አሁንም ደግሜ እናገረዋለሁ እነዚሁ ጋዜጠኞች ከሂሳብ ትምህርት ጥሩ አድርጎ የገባቸው መደመርና ማባዛት ብቻ ነው። አንድ ገበየሁ ውቤ ለአንድ ሺ የዘመኑ ጋዜጠኞች ተብዬዎች ይበቃል። ይህንንም ስናገር ታዲያ የተከበሩና በዘገባቸው የተደነቁና የሕዝብ ይሁንታ የተቸራቸውም የሉም ለማለት ግን አልደፍርምም፤ አይዳዳኝምም። ሁሉም ስራው ያውጣው!
አብረሃም ሊንከልን የተባሉት የተባባሩት አሜሪካ መንግስት የቀድሞ ፕሬዚዳንት የሳቸውን መንግስት የግብርና ዴፓርትመንት “ the people’s department,” ብለው ይጠሩት እንደነበር ከአንድ ” አሜሪካኖችና ግብርናቸው” ከሚል የቆየ መጽሔት ላይ አየሁት። እንግዲህ እንደሳቸው አባባል “ሕዝባዊ “ ማለታቸው አይደል። አዎን! ሕዝብ እየራበው፤ ጠኔ እያዳፋው፤ በምግብ እጥረት በሽታ እያንገላታው እያለ ስለ ሌላ ልማት ብንነግረው ትርጉም የለውም። በቂ ምግብ ካላገኘ የማሰብም፤ የመስራትም፤ የማምረትም፤ የመጀገንም አቅምና ታሪክ የመስራት ችሎታውም ይቀንሳል። ረሃብ ክፉ ነው። ቅስም ይሰብራል፤ ያስከፋል፤ ከሰውነት ጎዳና ያወጣል፤ ያሳፍራል፤ ያሰድዳል፤በመጨረሻም ይገድላል። ሕዝብ የመብላትም ሆነ ጤናውን የመጠበቅ ኃላፊነት ያለባቸው መንግስታዊ ተቋሞች ሁሉ ይህንን ኃላፊነታቸውንና ግዴታቸውን ተገንዝበው ነው ወደ ሥራቸው መግባት የሚችሉት እንጂ እንዲሁ ግድ የለሽ ሆኖ ሥራን መጀመር ያስጠይቃል።

ሌሎቹን ተቋሞችም እንዲሁ በጨረፍታ ወይም በወፍ በረር ቃኘት አድርጎ ማለፍም ተገቢ ነው። እነሆ! በጥቂቱ።

የግብርና ምርምር ተቌሞች

ከተመሰረተ ግማሽ ምዕተ ዓመት እያስቆጠረ ያለው የግብርና ምርምር ተቋም ዛሬ ላይ ራሱን በፈዴራልና በክልል በሚተዳደሩና በአገሪቱ የተለያዩ የግብርና ሥነ ምህዳር ቀጠና በመከፋፈል ምርምሩን እነደሚሰራ ይታወቃል። ዛሬ ቁጥሩ 55 የሚደርስ የምርምር ተቋም፤ ማዕከልና የሙከራ ጣቢያዎች እንዳሉት ይገለጻል። በመሠረቱ ምርምር ሁልጊዜ ከምርት ቀድሞ ይገኛል። ዛሬ የተገኘውን የምርምር ውጤት በአንድ ጀምበር ማሰራጨት አይቻልምም፤ አይታሰብምም። ነገር ግን የምርምሩ አካሄድ መሆን ያለበት በቅደም ተከተል የአገሪቱ ግብርና ዕድገትና ልማት ላይ ማነቆ በሆኑ ችግሮች ላይ ቅድሚያን ያስቀምጣል። መጨመር የምፈልገው ነገር ቢኖር ሌሎች አገሮች ጫፍ የደረሱበትንና የተራቀቁበትን እኛ ግን በሰለጠነ የሰው ኃይል፤ በመሳሪያዎች፤ በበጀት ዕጥረትና በአሰራር ደንብ ባልተዘጋጀንበት የምናስበውን ለጊዜው ትተን፤ ምርምሩ የአካባቢ ገበሬውን ዕውቀትና ክህሎት መሰረት አድርጎ ቢንቀሳቀስ ወደ ተግባር ለመለወጥ ያፈጥናል። ትኩረት ለሃገሪኛ ዕውቀትና ልንሰራ በምንችላቸውና ፈጣን ለውጥ ልናገኝባቸው፤ ወደ ተግባር በቀላሉ በሚመነዘሩት ላይ አትኩሮት ማድረግ ሳይሻል አይቀርም በማለት አስተያዬቴን በዚህ ተቋም ላይ ልቋጭ።

የግብርና ትራንስፎርሜሺን ኤጃንሲ

አዲስ የተቋቋመው የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲም ያዘጋጀውን ሰነድ መሰረት አድሮጎ መንቀሳቀስ ተቻለ መሰረት ለመጣል ደግ እርምጃ ነው። መቼስ በወረቀት የሰፈረና ያማረ ነገር የሃሳብ ነጸነት በሌለበት አገር ወደ ተመኘው ለመጓዝ እክል አያጣውም። ነገር ግን የመንግስት ዶማዎች፤ ቡሾች፤ “ቹሽኪዎች” እየቆፈሩ በአሰራሩ ለይ ማነቆ እንዳይሆኑበት ከፍተኛ ጥንቃቄ ያሻዋል። “ቹሽኪ” በቡልጋሪኛ ቋንቋ ቃሪያ ማለት ሲሆን ቃሉንም አንዳንድ እድሜ ጠገብና ነገር በምሳሌ ዕውቀታቸው ልክ ጥግ የደረሰባቸው አዋቂዎች ብቻ ይጠቀሙበታል። እንግዲህ በኛም ቢሆን ቃሪያ አንድም ይለበልባል፤ ያቃጥላል፤ ሰው ይፈጃል። ከፍ ሲል ደግሞ እንዲህ ” የበሬ አፍንጫ “ አይነቱ ትልቁ ቃሪያ ደግሞ ውስጡ ባዶ ቦሸቃ ስለሆነ መሰለኝ እኒያ ቡልጋዎቹ ይህንን የሚናገሩቱ። ሰለ ወደፊት ዕጣው በጎ ከመመኘት በስተቀር ለወቀሳ ገና ልጅ “ሙጫ” ነው። እንደ ስሙ ያድርግለትና ለውጥ ለማምጣት ያብቃው። ኤጀንሲውም አሜን እንደሚል ተወዲሁ ይታየናል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋሞች

የከፍተኛ ትምህርት ተቋሞችም በዘርፉ የተማረና የሠለጠነ የሰው ኃይል አምራቾችና አቅራቢዎ ች ስለሆኑም ልዩ ትኩረትን ይሻሉ።በትምህርቱ ዝግጅትም የሚያስተምሯቸውን ወጣቶች የኢትዮጵያ ግብርናን የሚገልጽ በኮርስ ደረጃ አዘጋጅተው እዚያው በትምህርት ላይ ሳሉ መተዋወቁ እጅግ አስፈላጊ ነው። ምሩቃኑ ወደ አገልግሎት መስጠት ሲሸጋገሩ በቀላሉ ችግር የመፍታት አቅማቸው ይዳብራል። አለባለዚያ እንደገና አዲስ ተማሪዎችና ሠልጣኞች ይሆናሉ። ትምህርት ቤቶቻችን የድምጻዊያንና የገጣሚያን ጥበ ብ ተሰጥኦ ያላቸውን ማሳያ መድረክ መሆኑ እንዳለ ሆኖ፤ ይህንኑ መሰረት በማድረግም ተማሪዎቻችን የሂሳብ ፤ የሳይንስ፤ የምህንድስና፤ የጤና፤ የምግብ ቴክኒዎሎጂና ሌሎች ተዛማጅ ዕውቀቶች ችሎታ ያላቸው መገኛ (መናኽሪያ ) መሆናቸውን ጭምር ማሳየት መቻል አለብን። ከበቂና ከተሟላ ዝግጅት ጋርም የተማሪውን ብዛትም ሆነ ጥራት ለማስተካከል ለአፍታ ቸል መባል የማይገባው ጉዳይ ነው። ብዛቱን ከጥራቱ ጋር ጎን ለጎን ለማስኬድ የሚያስችል አማራጭም አስቀድሞ እንዳለ መገንዘብ አለብን። በዚህ ጎዳይ ላይ አስተያየት የሚሰጡ ምሁራንን ሃሳብ አለመረጃ ማጣጣል ተገቢም አይደል፤ እንዲያውም ይወገዛል። አስተምራ የልጆቻን ዕውቀት የምታባክን አገር ብትኖር እምዬ ኢትዮጵያ ነች። የሰው ሃይልም በአግባቡ ካልተገለገሉበትም እንደ ሌሎቹ ሃብቶች ይባክናል፤ መቅኖ ያጣል። የወደፊቱ ምሁራኖች ተቀርጸው የሚወጡበት ማዕከልም በመሆኑ፤ ተማሪዎች በፍርሃት ሳይሆን በነጻነት ሃሳባቸውን የሚገልጹበት መድረክ መሆንም ሲችል ጭምር ነው። በአገራችን የመጀመሪያው የእርሻ ትምህርት ተቋም አምቦ ከተማ የሚገኘው የዛን ጊዜው የአምቦ እርሻና ቴክኒክ ትምህርት ቤት እንደሆነ ያውቃሉን? በ1939 ዓም እ ኢ አ የተመሰረተው ይኽው የእርሻ ትምህርት ቤት ፶ ኛውን የወርቅ ኢዬቤልዩ በወርሃ የካቲት 1989 አክብሯል። እኔም በቦታው ተገኝቼአለሁ። ፸፭ኛውን ለማክበር ደግሞ በ2014 ዓም ዕድሜ እንመኛለን። ቪቫ አምቦ እርሻ ተቋም!!! ዛሬ አምቦ ዩኒቨርስቲ።

የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅራቢ ድርጅቶች

ሌላዎቹ ደግሞ የግብርና ምርት ማሳደጊያ አቅራቢዎ ች ናቸው። የመሬት ማዳበሪያና ጸረ ተባዮች ኬሚካሎችን በማቅረብ ይታወቃሉ። በተለይ የመሬት ማዳበሪያ አቅራቢዎቹ በመንግስትና የፖለቲካ ፓርቲዎች ንብረት ናቸው። በገበሬው ልፋትና ኪሳራ ንግዳቸውን በትርፍ ያጣድፋሉ። ለገበሬው በተመጣጣኝ ዋጋ ያቀርባሉ ፤አያቀርቡም መንግሥትስ ገበሬውን በዋጋ ይደጉማል፤ አይደጉምም መረጃው የለኝም። ቀደም ሲል የነበሩት የግል አስመጬዎች ግን ከጨዋታው ውጭ እንደሆኑ የኢትዮጵያ አማልጋሜትድ ኃ/ተ/ማን ብቻ ማስታወሱ ይበቃል። በርካታ የግል ካምፓኒዎችም በጸረ ተባይ አስመዝጋቢነትና የተመዘገቡትን ጸረ ተበዮች ወደ አገር ውስጥ በፍቃድ በማስገባት ያከፋፍላሉ። ገበያ መር ላልሆኑ ገበሬዎች ግን አንዳንዶቹ ዋጋቸው ከገበሬው የመግዛትና የመጠቀም ጥቅም አንጻር ሲታይ በለው የሚያሰኝ አይዶለም ። ለኢትዮጵያ ገበሬዎች የተሻሻሉና የተመረጡ ዘሮችን በማቅረብ በዋናነት የሚታወቀው የኢትዮጵያ ምርጥ ዘር ድርጅት የሚባለው መንግሥታው ድርጅት ሲሆን በአነስተኛ መጠን ደግሞ የግልም እንዳሉ ይጠቀሳል። ቢሆንም የገበሬውን የምርጥ ዘር ፍላጎት በዓይነትም፤ በብዛትም ለማሟላት አልቻሉም። ዘርን በማምረትና በማከፋፈል እንቅስቃሴ መሳተፍ ለሚፈልጉ ባለ ሃብቶች መስኩ ብዙ ተወዳዳሪ የሌለበት መሆኑንም በዚሁ አጋጣሚ እገልጻለሁኝ። ባልተፈታው የመሬት ጥያቄ ምን ያህል ያስኬዳል? መልስ የለኝም።

የገበያ ሥርዓት ማስፋፊያ ድርጅቶች

የግብርና ምርት የገበያ ሥርዓት ምን ይመስላል የሚለውን ለመመልከት በቂ መረጃ ባይገኝም በገበያው ሥርዓት ገበሬው ላለመጠቀሙ ግን በተዘዋዋሪ መናገር ይቻላል። የቀድሞው የእርሻ ሰብል ገበያ ድርጅት አሰራር ግን በአምራቹ ገበሬ ላይ ተመልሶ እንዳይመጣ ለማስገንዘብ እንወዳለን። እ ሰ ገ ድ ገበሬውን እያስለቀሰና እንደ ኩዳዴ ወር (የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮች የሚጾሙት ነው) ድመት (ሰሞነኛ አባባል ነች። ቃሉን ከመገናኛ ብዙሃን እሰጥ እገባ ነው ያገኘሁት) እያከሳ ፤ዓይጥና ዓይጠ መጎጥ ግን እያኮራና እያወፈረ መኖሩን በጀብራሬዎች አንደበት ሲገለጽ እንደነበረው “ ኩራ እንደ እ ሰ ገ ድ ዓይጥ” እንደተባለው ዓይነት ጨዋታ ግን መስማት አንፈልግም። ለገበሬው ምርት በጥናት ላይ የተመሰረተ ዋጋ እንዲከፈለው እንጂ በርካሽ ዋጋ ተገዝቶ መንግስት ለሸማቹ ኅ/ሰብ ዋጋ ለማረጋጋት በሚል ሽፋን ብቻ ርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ለማጋበስ የሚደረገው ጨዋታ መቆም አለበት።

የመስኖ ልማት ድርጅት

የመስኖ እርሻ የሚሰጠውን ጥቅም ማውራት እንደው ለቀባሪው አረዱት እንዳይሆንብኝ ጥቂት ብቻ ልበል። የአሜሪካውን ካሊፎርኒያ ግብርና ያየ ደግሞ አብዛኞውን የካሊፎርኒያ ደረቅ ሸለቆዎችን እንዴት በቋሚተክሎች ፍራፍሬዎች፤ በአትክልቶች፤ በሩዝ ሰብል፤ በጥጥና በከብቶች መኖ ምርት አልምቶ የዛሬዋን ካሊፎርኒያ የግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ የ40 ቢሊዮን ዶላር ባለቤት አድርጎ በአገሪቱና በዓለም ደረጃ ቀዳሚ ስፍራ እንዳስያዛት መናገር ደግሞ አስፈላጊ ይመስላኛል። ስለኛ ግን መናገር የምፈልገው ነጥብ አለኝ። ይኽውም በመስኖ ልናለማው የሚችል በሚሊዮኖች የሚገመት መሬት እንዳለንና ይህም ስታትስቲክስ ከዘመነ ደርግ ብዙም ፈቀቅ እንዳላለ ነው የምንረዳው። የመስኖ ውሃ ለረዥም ጊዜ አገለግሎት ለይ በአግባቡ እንዲውል ካስፈለገ የመስኖ ሥራ መዋቅር በመስክ ላይ ማስቀመጥ ብቻ ሳይሆን ለውሃው አስተዳደርና ፍትሃዊ አጠቃቀም ከወዲሁ እንዲታሰብበት ለማስገንዘብ ጭምር ነው። የገጸ ምድርና የከርሰ ምድር ወሃ አጠቃቀም ነገን ጭምር ማሰብ አለበት። መንግስት እንዲህ ዓባይን ለመገደብና የኃይል አጠቃቀማችንን ከፍ ለማድረግ የሚሰሩትን ሥራም ጎን ለጎን የተገኘውንም ዕውቀትና ክህሎት ከግምት ውስጥ በማስገባት፤ ዋነኛው የሆኑት የውሃ ምንጫችን ወንዞቻችንን በመጥለፍ በዓመት ሁለቴና ከተቻለ ከዚያም በላይ እንድናመርት ቢያደርጉን ምንኛ በታደልን። አዋሽ፤ ባሮ፤ ጊቤና ግልገል ጊቤ፤ ሶርና ገባ፤ ዴዴሳ፤ ዳቡስ፤ ዋቢ ሸበሌ፤ ሻያ፤ ቦርከና፤ ጀማ፤ ጉደር፤ ያዩ፤ ፎገራ፤ የጨዋቃ፤ ኦሞና በዕውቀት ማነስ ምክንያት ያልጠቀስኳቸውን ሁሉ ጨምሮ በምድራችን በደጃፋችን አይደል የሚፈሱት።በእጃችንና በደጃችን ያለውን የውሃ ሃብትም ከምርጥ የአገሪቱ መሃንዲሶች ጋር መክረው መስኖ በመስኖ ቢያደርጉን ምን ገዶአቸው። ተው ስማኝ አገሬ ማለትስ ይዀው አይደለምን? በ1971ዎቹ የተጀመረው የአረንጓዴው ዘመቻ ያስከተላቸው ጥፋቶች ነገር ግን ምንም ያልተነገረላቸው የውሃ ሃብት አጠቃቀም ችግሮች ነበሩብን። እንዲህ ልግለጸው። የጨፌ መስኮችንና ረግረግ መሬቶችን በማጠንፈፍ ወደ ልማት ማምጣት በሚል አደገኛ ስልት ስንት እርጥብና ረግረግ መስኮችን አድርቀን ዛሬ ወደ ሜዳነት የለወጥናቸው ሥፍራዎች እንዳሉ አንባቢያን እንዲረዱልኝ፤ የልማት አርበኞቻችንም ግንዛቤ እንዲጨብጡልኝ ፈልጌ ነው። እርጥብ መሬቶችና ረግረግማ ሥፍራዎች ለወንዞቻችንና ለጅረቶቻችን መጋቢ አናት መሆናቸናውን እንኳን እኛ ድኩማን የግብርና ባለሙያዎቹ ግንዛቤ ሳንጨብጥ ፤ በአንድ ወቅት የኢሉባቦር ዋና አስተዳዳሪ ተብለው የተሾሙት በልማት ስራቸውና ሕዝብን በልማት ማሰማራት ዋና ሃይል እንደነበር በአመራራቸው የታወቁቱ አቶ አንሙት ክንዴ በአንድ የግብርና ልማት እንቅስቃሴ ሥራ ዓመታዊ ግምገማ ላይ ነበር የኛዎቹ የግብርናው ልማት ስራ መሪዎቹ ረፖርታቸውን ሲያቀርቡ ልክ ግዳይ እንደጣለ አንበሳ ይሄንን ያህል የጨፌና ረግረግ መሬት ወደ ልማት አመጣን እያሉ ለተሰብሳቢው ሲደሰኩሩ አዳምጠው ጉዳዩ ልማት ሳይሆን ለነገው የውሃው ሃብታችን የጥፋት መጀመሪያ መሆኑን በመብለጥ የተናገሩት። የአለም ማያ፤ የአደሌና የላንጌ ሐይቆች፤ አናታቸው የጨፌ መስክ የነበሩት የሐረር ሐማሬሳ ከተማ ከበው ወደ ፈዲስ የሚፈሱት ሁለት ወንዞችና የኢሉአባቦር እርጥብና ረግረግ መሬቶች ዛሬ ደርቀውና አንዳንዶቹ በአደገኛ ሁኔታ ላይ ለመገኘታቸው ለእኔ ዓይነተኛ ምሳሌዎችና አስረጅ ናቸው። እንክብካቤና ጥበቃ ለርጥብና ረግረግንም ሥፍራዎች ጠቃሚና ዓይን ከፋች ስልት ነው።

የገጠር መሬት ሃብት አስተዳደር ተቋም

የኢትዮጵያ መሬት የኢትዮጵያውያን አንጡራ ሃብት በመሆኑ አገልግሎቱም በቅድሚያ ለኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች መሆን ይገባዋል። ኢትዮጵያዊያን በመሬታቸው የበቀሉትን ምርቶች ቅድሚያ ተጠቃሚ እንጂ ተመልካች መሆን የለባቸውም። አገራቸው ያፈራውን ምግብ እነርሱ ሳይቀምሱና ሳያጣጥሙ የሌላ አገር ሰዎችን መቀለብ ከሞራል ጥያቄም ባሻገር መብታቸው መሆኑን አስረግጬ መናገር እሻለሁ። ግብርናውን ለማዘመን በሚል ፈሊጥ ለዘመናት በመሬቱ በዘልማድ መንገድ ሲንከባብና ለምነቱን ሲጠብቅ የኖረውን አገሪኛ ሰዎች እያፈናቀልን ለውጭ ኢንቨስተር መሬትን የሚያክል ንብረት እዚህ ግባ በማይባልና የነዋሪውን ጥቅም ባላገናዘበ መልኩ የሚካሄደው የመሬት መቀራመት የኋላ የኋላ የሚጎዳው አገርና ሕዝብ ነው። ጥቂት ባዕዳንን ሃብት በሃብት ላይ እንዲጨምሩ ብቻ በማሰብ፤ድሃን ከሚወዳት መሬቱ ማፈናቀል ሃጢአት ነው። የሕዝቡን ህልውናና ደህንነት ሳይሆን እያስከበርን ያለነው በላዩ ላይ አደጋና ተጨማሪ ስጋት ነው እያስቀመጥን ያለነው። በተጨማሪም በስራ ፈጠራና በቴክኖሎጂ ሽግግር ስም ጥቂቶች እንዲከብሩና የሃብት ደረጃቸውን ከፍ ባማድረግ የሚቀመጡበትን ልክ እንጂ ያሻሻልነው የሕዝቡን የምግብ ዋስትና አይደለም እያረጋገጥን ያምንገኘው። ሃብት ፈጣሪው ሕዝብ ይሄ ስንኩልና ጎዶሎ አሰራር ይጎዳዋል፤ በአገሩም ባይተዋርና የበይ ተመልካች ያደርገዋል። ከልቡም ልማት ተብዬው እንቅስቃሴም አያሳትፈውም። የውጭ ኢንቨስተመንት በሌሎች የስራ መስኮች ተጨማሪ ሃብት ማስገኘት ይቻል ይሆናል። በግብርናው ክፍለ እኮኖሚ ግን በተለይ ከመሬት ጋር በተገናኘ ላይሰራ ይቻላልና ጠንቀቅ ማለቱ ከፖለቲካ ዝርክርክነትና አስቸጋሪነት አንጻር ሲታይ ማለፊያና ይበል የሚያስኝ ሙያ እንዳይደለ መሬቱን እየቸረቸሩት ለሚገኙት የመንግስት ተቋም ሹመኞችና ጥቅመኞች ጉዳዩን በትኩረት እንዲመለከቱት ይሁን ስል እጠይቃለሁ። እስከዛው ግን መስራት በምንችለው አቅማችን ቅድሚያ ለኢትዮጵያዊያኑ ይሁንልን። ለውጭ ባለ ሃብት የከፈትነውን ዕድል ሳናጓድል የአገሪቱን ባለሃብቶች እንዲጠቅም አድርጎ ማሳተፉ ተገቢ ነው።

የሙያ ማኅበሮቻችን

በአገሪቱ በርካታ የሙያ ማኅበሮ ች አሉ። ለመጥቀስም፦ የሰብል ሳይንስ፤ የአዝርዕት ጥበቃ፤ የኢኮኖሚክስ፤ የየደን ልማት፤ የእርሻ መሃንዲሶች፤ የምግብ ጥናት፤የጤና፤ የገበያ ጥናት፤ የሥነ ሕይወት፤ የአፈር ሳይንስ፤ የኮንስትራክሺን፤ የሜካኒካል መሃንዲሶ ችና ሌሎችም። አንዳንዶቹ ዕድሜ ጠገብ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ገና ሙጫ ናቸው። የምግብ ዋስትናቸው ከእድሜያቸው አንጻር ገና አልተሟላም። በምግብ እጦት፤ በጠኔ፤ ችጋርና ድርቅ ምክንያት በእድሜያቸው ማስመዝገብ ያለባቸውን ቁመትም ሆነ ክብደት ገና አልደረሱበትም። ዓመታዊ ጉባኤ ያካሂዳሉ፤ የምርምርም ሆነ የልማት ጥናት ወረቀቶች ይቀርባሉ። ውይይት ይደረግባቸዋል፤ ጥያቄዎች ይቀርባል መልስ ይሰጥባቸዋል። ዕውቀት ይጨምራል፤ ልምድ ይካበትበታል፤ ማን ምን እንደሆንና ምን እንደሚሰራ ይታወቃል። ጥሩ ነው። ዕውቀት ለብቻው ከሆነና ወደ ተግባር በሰንካላ አመራርና ፖሊሲ ካልተተረጎመ እንደምን ይጠቅማል? ምሁራን ስለሙያቸው ዋጋ ትክክለኛውን ካላወሩበት፤ የተሳሳተውን ካላስተካከሉበት፤ ሁሉ ነገር ፖለቲካ ነው ብለው ካመኑበት፤ ዕውቀት ከጋን ውስጥ መብራትነት አልወጣችም ማለት ነው። ትምህርት ለምርምር ለምርትና ለችግር መፍቻነቷ ታዲያ ለመቼ ነው? ምነው ስለ ሙያችን አንደበታችን ተዘግቶ የፓርቲ ፖለቲከኞች ስለ ሙያችን ደግመው ሲያስተምሩን ለመማር ፍቃደኞች ሆንን? በሙያችን ቀድመን መታየት ሲገባን ዛሬም ተማሪዎች ነገም ተማሪዎች ሆነን መታየት ፈለግን? ዕውቀታችንን መሰረት አድርገንማ ሃሳባችንን መግለጽና ማብራራት ካቃተን አካላችንንም ሆነ ኀሊናችንንም ጭምር ምርኮኛ አድርገናል ማለት ነው። እግዚኦ ከዚህስ ይሰውረን! ካለፈ በኋላስ ቢናገሩት ማንን ሊጠቅም? ትንሽ፤ ትንሽ ካሁኑ ጀምሮ እንናገር። ትንሽ ትንሽ መስዋዕት እንሁን። እንግዲህ ሺ ዓመት አይኖር።

መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች

ከዚሁ የግብርና ክፍለ ኢኮኖሚ ጀርባ ደግም መንግስታዊ ያልሆኑ የሚባሉ ምግባረ ሠናይ ድርጅቶች አሉ። በንጉሱ ጊዜ በቁጥርብዛታቸው በአስራዎቹ ሲገመቱ፤ በደርጉደግሞ በመቶዎቹ ነበሩ። ዛሬ ግን ቁጥራቸው ከ1500 በላይ እንደሆኑ በቅርቡ የኢሳ ቱ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና እንግዳ አድርጎ ያቀረባቸው ባለሙያ በቃለ መጠይቅ ወቅት መግለጻቸው ይታወሳል። አብዛኛዎቹ በገጠር የሚገኘውን የሕዝብ ክፍል ለመርዳትና በአኗኗሩ ላይ ለውጥ ለማምጣት የተሰለፉ አጋዥ ኃይሎች ናቸው። በሰብል ልማት፤ በውሃና አፈር አጠባበቅ፤ በአነስተኛ መስኖ አገልግሎት፤ በደን ልማት፤በሰብል ዘርና ሌሎች የተክል መራቢያ አካሎች በማቅረብ፤ በጤናውና በኑሮ ዘዴውና በሌሎችም ለተጠቃሚው አገልግሎ ቶችን በማቅረብ ይታወቃሉ። አገልግሎታቸው ምን ያህል ጠቅሟል የሚለው ውስጥ ለመግባት ሌላ ክትትልና ጥናት ስለሚያስፈልገው እዚያ ውስጥ የምገባበት ችሎታውም አቅሙም የለኝ። እዚሁ ዘንድ ላቁም። ብቻ ከገበሬው ኑሮ ጋር እንደተሰለፉ ለመግለጽና ለመረጃ ያህል ነው ያቀረብኩት።

ታዲያ ይህ ሁሉ የተቋምና የሰው ሃይል ተሰልፎና ተግባሩን ካከናወነ ለምንድነው ከዚህ አ ስከፊና ጎስቋላ ኑሮ እኛ ኢትዮጵያዊያኑ መውጣት ያቃተን? የኔም፤ የናንተም ፤ የሌሎችም የኛን ችግር መስማት የሰለቻቸው የዓለም ህብረተሰብ ክፍሎች ዋነኛ ጥያቄ ነው። አገራችንን ሁላችንም በምንፈልገው ና በወደድነው መልኩ ተርጉመናታል፤ ተረድተናታል። ቁም ነገሩ ግን ያለው መለወጥ (ቃሉን ጠበቅ ተደርጎ ይነበብ) መቻሉ ላይ መሰለኝ።

ለማጠቃለል ሙከራ እናድርግ። ላለፉት 6ትና 7 ዓመቶች መሰረታዊ የሚባሉት የምግብ እህሎችና ውጤቶች ዋጋቸው በፍጥነት ዕለት በዕለት እየናረ አይቀመሴ ደረጃ ለይ ደርሷል። በውጤቱም በሚሊዮን የሚቆጠሩት የኅብረተሰብ ክፍሎች በልቶ ማደር ምኞት ሆኖባቸዋል። የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሰማይ ያህል እርቋቸዋል። ትናትን ማመስገን ከተጀመረ ሰነባብቷል። ኑሮ ተወደደ፤ መብላት አልቻልንም የየዕለት የሕዝብ እሮሮ ነው። ጋሽዬዎችና አባቶች ኪሳቸው ባዶ ነው፤ እትዬና እናቶችም የእጅ ቦርሳቸው ለስሙ ነው ያለው። ደፍሮ የመግዛት አቅማቸው ተሟጧል። ጥያቄው ከገዢዎችችን መልስ ጋር አልተጣጣመም። የጥያቄው መልስ በተጓዳኝ መስመሮች መንገድ ላይ ነው እየተጓዘ የሚሄደው። ተጓዳኝ መስመሮች አይነካክም፤ አይገነኙም። ጉዟቸው አይደረሰበትም፤ የትዬሌሌ ነው። ምግብን በገበያ ላይ ማየት እንጂ ገዝቶ መጠቀም አቅም ቀን በቀን እየተሸረሸረና እየጠፋ ነው።

ምግብ መብት ነው ተብሎ አገሮች ሁሉ መሰረተ ሃሳቡን ከተቀበሉትና ያንንም ለመተግበር በየዓመቱ መሃላና የድርጊት ፕሮግራም ከተነደፈለትም ሰነባብቷል። በርግጥም ሰናስበው ደግሞ መራብና በችጋር ጠኔ ስቃይ ማየትም መብት ነው ብሎ የሚከራከር ጤናማ አእምሮም ያለው ሰው ያለም አይመስለኝም። ያለመራብ መብት እንጂ የመራብ ግዴታ የለብንም። ባጭር አገላለጽ መራብን የሰው ልጆች ሁሉ ሊጠሉትና ልንጠየፈው የሚገባ ውጉዝ ሁነት ነው። ዱሮ እንደምናስበው የ 40 ቀን ዕድልና ዕጣም አይደለም፤ የእግዜርም ቁጣም ሊሆን አይችልም። እንደ ዜጋ ሁሉም ሰዎች ለኑሯቸው የሚበቃ አስፈላጊውን አልሚ ምግቦ ች የያዘ ምግብ ማግኘት አለባቸው። ምግብ መብት ነው ሲባል ደግሞ መንግስት የሚባለው ተቋም በየቤቱ እየዞረ ምግብ ያድል ማለትም አይደለም። ነገር ግን በዋናነት ሰው በፈጠረውም ሆነ በተፈጥሮ አደጋ ችግር ምክንያት በጊዜያው፤ በአጣዳፊና ሥር በሰደደ የምግብ እጦት ችግር ሰለባ የሆኑትን የኅብረተሰብ ክፍሎች አለምንም አድልዎ ሰው በመሆናቸው ብቻ መታደግ እንዳለበት ለመግለጽ ነው። የመንግስት አንዱ ተግበር በግዛቱ ውስጥ የሚኖሩትን የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ደህንነትና ጤናቸውን መጠበቅ ነው። ይህም በመሆኑ መንግስት ለአሰራር ያመቸው ዘንድና ተጠያቂነቱንና ኃላፊነቱን በአግባቡ ለመወጣት የምግብ ዋስትና ሕግና ደንብ አውጥቶ ካለምንም አድልዎ መተግበር አለበት። ለዜጎቹ መራብና መጎሳቆል ሃላፊነቱ የመንግስት እንጂ የሌሎች እንዳልሆነ ጠንቅቆ ማወቅ ያሻዋል። የኢትዮጵያ ምድር አንዱ በልቶና ጠግቦ የሚያደርገውን ያጣበት ሌላኛው ደግሞ ረሃብን እያሰበና እየተጨነቀ የሚኖርባት ምድር መሆኗ ማቆም አለበት። ምግብ አንዱን ወገን ጠቅሞ ሌላውን መጉጃ መሳሪያ መሆን የለበትም። ክቡሩን የሰው ልጅ ማስራብና በጠኔ ማንገላታት ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ስለሆነ ” ውጉዝ ከመአርዮስ” መባል ያስፈልገዋል። ወንጃልም ስለሆነ እንደየደረጃው ያስጠይቃል፤ ብያኔም ያሰጣል ፤ ያሳስራል፤ ምህረትም አያሰጥም፤ ከፍም ካለ በሞት ያስቀጣል። ድሃን መርዳት እንጂ በረሃብ መቅጣትም በሃይማኖቱም አስተሳሰብ ቢሆንም ኩነኔ ና ሃጢአት ነው። ከአካል ሞት በኋላም ላለው መንፈሳችን በመንግስተ ሰማያትም አያስገባምም ፤ እንዲያውም በጀሃነም ያስቀጣል። በአንድ አገር፤ ክልልና ቀዬ የሚኖሩ ሕዝቦች እንዲህ ቅጥ ያጣ የተመሰቃቀለ ኑሮ የሚገፉበት ዐብይ ምክንያት የፖለቲካው ምስቅልቅልና በጥቅም የተሳሰረ የኢኮኖሚ መዋቅር በመሆኑ፤ ይህ ችግር ሳይቃለለ የምግብ ዋስትናን ከቃላት ባሻገር ልናገኘው እንደማንችል መገንዘቡ ጠቃሚ ነው። ጠቅለል ባለ አነጋገር የምግብ ዋስትና ችግር ምርት በመጨመር በሚደረገው ሩጫ ብቻ የሚፈታ ሳይሆን ፖለቲካዊም ችግር ጭምር ነው። ፖለቲካ ደግሞ ሰው ሰራሽ ነው። ስለሆነም ፖለቲካዊ መፍትሄ በሰዎቻችን መልካም ፍቃድ ያስፈልገዋል ማለት ነው። የተዝረከረከና የተጨማለቀ፤ የተወሰኑ ቡድኖችን ጥቅም ብቻ ለመጠበቅ የቆመ ፖለቲካ ደግሞ ችግሩን ሊፈታ የሚያስችል ተቋማዊም ሆነ ሰዋዊ አቅምና ችሎታ የለውም፤ አይጠበቅምም።

ሌላው ሳልጠቅሰው ማለፍ የማልፈልገው ነጥብ ደግሞ የመሬት ባለቤትነት ጥያቄን ጉዳይ ነው። ለገበሬው ያለችው አንድ ትልቁ ሃብት መሬት ብቻ ናት። ገበሬው የመሬቱ ባለቤት ከሆነ ንብረቱን ጥሎ ከተማም አይሰደድም። ማነው ሃብቱን ንብረቱን ጥሎ ንብረት አልባ ለመሆን የሚመኘው። እንደውም ብዙ እንዲያመርት እንደ ማትጊያ ዘዴ ይሆነዋል። የኪራይ ንብረት ሲሆን ግን ያልተሟላ ዕለት ሲመጣ ጥሎት ወደ ከተማ ይሰደዳል። ገበሬም እንደኛው ሰው ነው፤ነገን ከኛ በተሻለ ያስባል ፤ ስኬታማ ኑሮን ለመኖር ይታገላል፤ ይጥራል። በዚህ ጉዳይ ላይ የገበሬው ድምጽና ፍላጎት ይጠና ፤ ይጠየቅ። ገበሬውም ድምጹን የሚያሰማበት የራሱ ብቻ የሆነ ማኅበርም ከቀድሞዎቹ የገበሬ ማኅበር በተለየ ሁኔታ በራሱ አነሻሽነትና ጥያቄ መመስረት አለበት። ከመንግስት ሰዎች የሚጠበቀው ደግሞ የመሬት ይዞታውን ማሻሻል እንጂ ማጃጃል መሆን የለበትም። የበለጠ የገጠሩን ኑሮ ምቹ ካደረግንለት ወደ ከተማ ስደት አይጠበቅም። የከተማ ከንቲባዎቻችን ከተሞቻቸውን ለኑሮ ምቹ እንዲሆኑ እንፈልጋለን የሚሉትን ዲስኩር በገጠሩ ማስፋፋት ይጠበቅብናል። ገበሬን በሽታ እንዳይነካው ጤንነቱን በቅርብ እንጠብቅለት። ገበሬ ሲታመም፤ አገርም ይታመማል። መሬት ጦም ማደር ትጀምራለች። ጦም ያደረ መሬት የሚያበቅለው አረሞችን ነው። ገበሬም አይሙት፤ የሞተ እንደሆን ዕውቀቱንና ክህሎቱንም ጭምር ይዞ ነው የሚሞተው። የዕውቀትና የክህሎት ድርቅ ደግሞ ውጤቱ አስከፊ ነው። ምች ይመታናል፤ አጠውልጎም ያጠፋናል። እግዚዎ! መሃረነ ክርስቶስ! ጸሎቱን ጨርሱ። እኔስ አበቃሁኝ ያሰብኩትን ቢሆንም ባይሆንም፤ ቢያስከፋም ቢያስደስትም ተነፈስኩኝ። አሜን!!!!!
በሌሎች መጣጥፍ ዐርዕስት እስከምንገናኝ ጤና ይስጥልኝ!!!
ሠሎሞን ታምሩ ዓየለ

ህወሓቶች በዓረናና በትግራይ ህዝብ የተቃውሞ መንፈስ ደንግጠዋል፤ “እኛ ካልተመረጥን የትግራይ ማንነት ይጠፋል”እያሉ ነው

0
0

አብርሃ ደስታ

አብርሃ ደስታ

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ እንደዘገበው፦

ህወሓቶች በዓረና እንቅስቃሴና በትግራይ ህዝብ የተቃውሞ መንፈስ በጣም ደንግጠዋል። የዓረና ተከታታይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ተከትሎ ህወሓትም ተከታታይ ህዝባዊ ኮንፈረንስ ለማድረግ ወስኗል፤ ጀምሯልም። የህዝብ ተወካዮች ተብለው የተመረጡ የየአከባቢያቸው ህዝብ እንዲሰበስቡ መመርያ ተሰጥቷል። ይቅርታ የህዝብ ተወካዮች ሳይሆኑ የፓርቲ ተወካዮች መባል አለባቸው፤ ምክንያቱም የተመረጡት በህዝብ ሳይሆን በህወሓት ነው። የሚያገለግሉትም ለህዝብ ሳይሆን ለህወሓት ነው። ምክንያቱም በህዝብ ተመርጠው ተብለው የህዝብ ችግር ከመናገር ይልቅ የህወሓት አጀንዳ ደግፈው የሚያጨበጭቡ ናቸው። እስካሁን የመረጠውን ህዝብ ችግር የተናገረ የህዝብ ተወካይ የህወሓት አባል አላገኘሁም። በህወሓት የፖለቲካ ፍልስፍና የተማእከለ ዴሞክራሲ መሰረት አንድ አባል ከፓርቲው አስተሳሰብ ወጥቶ የፓርቲው ብልሹ አሰራሮች ባደባብይ ወይ በፓርላማ ማጋለጥ አይችልም። ካጋለጠ ከፓርቲው ይባረራል። ለዚህም ነው የህዝብ ተወካዮች ተብለው ፓርላማ ይገቡና የፓርቲው ተወካዮች ሁነው የሚቀሩ።
Arena-Tigray-logo
የህዝብ ወይም የህወሓት ተወካዮች ህዝብ ሲሰበስቡ ፈተና እያጋጠማቸው ነው። የሽረ ተወካይ ህዝቡ ሰድቦ አባሯታል። ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ በዓድዋ ህዝብ ተሰድባለች። የዓድዋ ህዝብ ለቅዱሳን “እናንተ ቤተሰቦቻቹ ለመርዳት እንጂ መቼ ለህዝብ ደህንነት ሰርታቹ ታውቃላቹ?” የሚል አስተያየት ሰጥቷል። በመቐለም አዲሳለም ባሌማ ህዝብ (ይቅርታ በመቐለ ህዝብ ተብለው የተሰበሰቡ ካድሬዎች ነበሩ) ሰብስቦ እርዱን ማለቱ ታውቋል። የመቐለ ዉሃ በ2007 ዓም ፕሮጀክት ቀርፀን እንፈተዋለን፤ ብቻ እኛን ምረጡ ብሎ ተማፅኗል። የመቐለ ነጋዴዎች ሰብስቦ ችግሮቻቹ ለመፍታት ተዘጋጅተናል ብሎዋል።

አጠቃላይ የህወሓት ስትራተጂ ህዝብን ለመሸወድ ያለመ ሲሆን የሚያጠነጥነውም “ህወሓት ካልተመረጠ የትግራይ ማንነት ይጠፋል” የሚል ነው። “ጠላቶቻችን እየመጡ ናቸው፤ ከህወሓት ጎን ተሰለፉ! ጦርነት ሊከፈትና ልጆቻችሁ አደጋ ላይ ሊወድቁ ይችላሉ” እያሉ ይገኛሉ።
ግን የትግራይ ማንነት በህወሓት ህልውና የተንጠለጠለ አይደለም። እንኳን የህዝብ ማንነት የአንድ ግለሰብ ማንነትም ሊጠፋ አይችልም። ምክንያቱም የህዝብ ማንነት ቀርቶ የአንድ ሰው ማንነት ከጠፋ የሰውየው መብትና ነፃነት ተጥሷል ማለት ነው። መብቱ ወይ ነፃነቱ ከተጣሰ ደግሞ አዲስ የመጣ ስርዓት ልክ እንደ ህወሓት አምባገነናዊ ስርዓት ነው ማለት ነው። የህውሓትን ያህል አምባገነን ስርዓት ከመሰረትን ደግሞ ህወሓት አልተቀየረም ማለት ነው። ህወሓት ካልተቀየረ የፖለቲካ ለውጥ አልመጣም ማለት ነው። የፖለቲካ ለውጥ ካልመጣ ደግሞ ትግላችን ይቀጥላል (ለውጥ እስኪመጣ ድረስ)። ስለዚህ እኛ የምንታገለው ከህወሓት የተሻለ ስርዓት ለመመስረት እንጂ ህወሓትን በሌላ አምባገነን ስርዓት ለመተካት አይደለም። ስለዚህ ላረጋግጥላቹ የምፈልገው ነገር ቢኖር የማንም ህዝብ ወይ ግለሰብ ማንነት ይከበራል እንጂ አይጠፋም።

“ጠላቶቻችን እየመጡ ነው” የሚለው ዉንጀላ ግዜው ያለፈበት ፕሮፓጋንዳ ነው። የህዝብ ጠላት ጨቋኝ ስርዓት ነው። ህዝብ ከጨቋኝ ስርዓት ዉጭ ሌላ ጠላት የለውም። ጨቋኝ ስርዓት የህዝብ ጠላት እስከሆነ ድረስ እንታገለዋለን። ጨቋኝ ስርዓት ምን ግዜም አንቀበልም። ጨቋኝ ስርዓት ስለማንቀበል ነው አሁን ህወሓትን የምንቃወመው። ስለዚህ ዓላማችን የስርዓት ለውጥ ማምጣት እስከሆነ ድረስ ለጨቋኞች ቦታ የለንም፤ ህወሓትም ሌሎችም። እኛ የምንቀበለው ዴሞክራሲያዊ የህዝብ መንግስት ብቻ ነው።

(ከዚህ ቀደም የአረናን ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳይሳተፉ የተከለከሉ የሽሬ ነዋሪዎች - ፎቶ ከአብርሃ ደስታ) - ፎቶ ፋይል

(ከዚህ ቀደም የአረናን ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳይሳተፉ የተከለከሉ የሽሬ ነዋሪዎች – ፎቶ ከአብርሃ ደስታ) – ፎቶ ፋይል


ህወሓቶች በዓረና አጀንዳዎች በመስጋታቸው ምክንያት የዓረና ሐሳቦችን ለመቀበል እየተገደዱ ነው። በቅርቡ በህዝብ ፊት እየቀረቡ የመሬት ይዞታ ጉዳይ በዓረና እየቀረበ ያለውን ሐሳብ እንደሚደግፉ እየገለፁ ነው። (የዓረና ሐሳብ እንደግፋለን እያሉ ሳይሆን የህዝብን ፍላጎት ለማሟላት እንሞክራለን በሚል ነው። የህዝቡ ፍላጎት ደግሞ የዓረና የመሬት ፖሊሲ ነው)። የዓሰብ ወደብም በሰለማዊ መንገድ ለማስመለስ እንሞክራለን በማለት እየተመፃደቁ ነው። ለነጋዴዎችም ግብር እንቀንሳለን በሚል ምክንያት ለመጀንጀን እየሞከሩ ነው።

አሁን ግራ ሲገባቸው ስራ የሌላቸው ወጣቶች ለውትድርና ለመመልመል እየሞከሩ ሲሆን ማንም ወጣት ፍቃደኛ ሊሆን አልቻለም። በወጣቶቹ ዉሳኔ የተደናገጡ ህወሓቶች የጎዳና ተዳዳሪ የነበሩ ህፃናት ልጆች አታለው (ስራ እንሰጣቸዋለን በሚል ምክንያት) ለዉትድርና መመልመላቸው ታውቋል። ለምሳሌ በመቐለ ከተማ የነበሩ ብዙ የጎዳና ተዳዳሪ ህፃናት ተወስደዋል (ማረጋገጥ ይቻላል፤ አሁን በመቐለ ከነበሩ ህፃናት አንድ የቀረ የለም)። ግን አብዛኞቹ ህፃናት ከ16 ዓመት በታች ናቸው። ከ16 ዓመት በታች ህፃናት ለውትድርና የሚመለምል የቸኛ ሕገወጥ መንግስት ኢህአዴግ መሆኑ አይቀርም። ምክንያቱም በማንኛውም ሕግ ከ16 ዓመት በታች ህፃናት ለውትድርና መመልመል ሕጋዊ ሊሆን አይችልም። ጉዳዩ የሚከታተለው ካገኘ በዓለም አቀፍ ሕግ ወንጀል ሊሆን ይችላል።

በዓዲግራት የፈፀሙብንን ድብደባ በጣም አክስሮባቸዋል። የትግራይ ህዝብ ሙሉበሙሉ እንዲጠላቸው ሁነዋል። እናም በጣም ሰግተዋል። በቅርቡ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሊጀምሩ ይችላሉ። በወታድሩም ቢሆን ህወሓቶች ድጋፍ የላቸውም።

አንዳንዴ ኑሯችን በራሳችን እንድንቀልድ ያስገድደናል (ዳዊት ከበደ ወየሳ)

0
0

addis ababa
(ዳዊት ከበደ ወየሳ)

አንዳንዴ ኑሯችን በራሳችን እንድንቀልድ ያስገድደናል:: ካለፉት በርካታ አመታት ጀምር በአዲስ አበባ የሚታየውን የመብራት መቆራረጥ የተመለከተ ሰው በሙሉ ያዝናል:: ይህ ሃዘን ወደ ብሶት ቁጣ ተቀይሮ ሰሞኑን በተከታታ ህዝቡ በመብራት ሃይል ላይ የተቃውሞ ሰልፍ በማድረግ ቁጣውን እየገለጸ ነው:: አንድነት ፓርቲም ይህን አስመልክቶ “የ እሪታ ቀን” ብሎ የሰየመውን የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ እንቅስቃሴ ጀምሯል:: እኛ ከውጭ ሆነን ነገሮችን ስንመለከታቸው እውነት የማይመስሉ እውነቶችን እያየን መገረማችን አልቀረም:: ይህንን ግርምት በቀልድ ቢጤ ብናዋዛው ብለን ስናስብ ደግሞ የሜትሮሎጂ አየር ትንበያ ታወሰን:: መብራት ሃይል በሜትሮሎጂ ዜና አይነት የሰሞኑን የመብራት መጥፋት እና መጥፋት ዘገባ ምን ብሎ ቢያቀርብልን ይገርመናል:: እስኪ በራሳችን እየሳቅን የመብራት ሃይልን… ሜትሮሎጂያዊ ዜና ከዚህ በታች እናንብብ::

የሰሞኑ የአዲስ አበባ የመብራት ሃይል… ይቅርታ የመጥፋት ሃይል ትንበያ ከዚህ በመቀጠል ይቀርባል:: በሰሜን አዲስ አበባ… ከበላይ ዘለቀ ጎዳና እስከ ፒያሳ፣ ውቤ በርሃ፣ አራዳ፣ ዶሮ ማነቂያ፣ ሰራተኛ ሰፈር፣ ከቸርችል ጎዳና እስከ ቴዎድሮስ አደባባይ ድረስ መጠነኛ የሆነ የመብራት መቆራረጥ ይደርሳል:: ከዚያ ወረድ ብሎ በስቴዲየም እና አካባቢው, መስቀል አደባባይ, ከእስጢፋኖስ እስከ መገናኛ 22 ማዞሪያ እና ኮተቤ ድረስ… እንዲሁም በካዛንቺስ አካባቢ ደብዛዛ እና ፈዛዛማ የመብራት ብርሃናት ይታያሉ::

በቦሌ እና ቦሌ ቡልቡላ መብራት እንደበጋ መብረቅ ብልጭ ድርግም ይላል:: ከላፍቶ እስከ ሳሪስ; ወሎ ሰፈር፣ ጎፋ ማዞሪያ፣ ቄራ፣ ሳር ቤት፣ እንዲሁም ከአየር ጤና እስከ ሜክሲኮ አደባባይ ነጎድጓዳማ የመብራት መቆራረጥ ያጋጥማል:: በጨርቆስ እና አካባቢ… እንደከዚህ ቀደሙ ደረቅ አየር እና ድፍን ጨለማ ሆኖ ይሰነብታል::

የአዲስ አበባ ምእራባዊ ዞን… ከተክለሃይማኖት ሰፈር ጀምሮ በአብነት አድርጎ እስከ ሰባተኛ እና መርካቶ ድረስ፣ መሳለሚያ፣ ኮልፌ ከዊንጌት እስከ ቡራዩ ድረስ ምንም አይነት የኤሌክትሪክ ስለማይኖር ከመብራት አደጋ ነጻ ይሆናሉ::

በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን፤ በተለይም የንግዱ ህብረተሰብ ይህንኑ አውቆ አካባቢ በካይ የሆኑ የናፍጣ ጄነሬተሮችን እንዲጠቀም እናሳስባለን:: የባንክ አገልግሎት ሰጪዎች፣ የኮምፒዩተር ቤቶች… መብራት ቢመጣም እንኳን ኔትዎርክ ስለሌለ፤ ጽጉር ቤት እና ምግብ ቤቶችም… መብራት ብንሰጣችሁ ውሃ ስለማይኖር፤ ይህንን ተግዳሮት ግምት ውስጥ በማስገባት ነፋሻማ የሆነውን ቫት እና መብረቃማውን የሽያጭ ታክስ በመክፈል የዜግነት ግዴታችሁን እንድትወጡ ከወዲሁ እናሳስባለን::

በአጠቃላይ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች ምሽቱን ጧፋማ፣ ኩራዛማ እና ሻማማ በመሆን ይሰነብታሉ:: ዛሬ ከሳተላይት ያገኘነው ተንቀሳቃሽ ምስል እንደሚያሳየው… አዲስ አበባ ከላይ ወደ ታች ስትታይ እንደክሪስማስ ዛፍ ብልጭ ድርግም ትላለች:: በዚህም ምክንያት ምሽት ሲሆን; አዲስ አበባን በአነስተኛ አውሮፕላን የሚጎበኟት ቱሪስቶች ቁጥር በእጥፍ ጨምሯል:: ከዘርፉ የሚገኘው የገቢ መጠን በመጨመሩ መንግስት ለዚህ አዲስ የስራ መስክ ትኩረት በመስጠት የማበረታቻ ገንዘብ እንደሚመድብ አስታውቋል:: ለስራውም መሳካት… መብራት ሃይል የሰፈር መብራቶቹን በፈረቃ በማብራት እና በማጥፋት; ምሽቱን “በብልጭ ድርግም” የሚያደምቀው መሆኑን በደስታ ገልጿል::

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live