Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ከለባን ከተማን ወደ ትግራይ ክልል ለማካለል የተነሳውን እቅድ በመቃወም በአፋር ከፍተኛ ንቅናቄ ተጀመረ

$
0
0

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)


በአፋር ክልል የምትገኘው በወርቅ እና በፖታሺየም እንዲሁም በተለያዩ ማእድናት የበለጸገችውን የኮለባን ከተማን ወደ ትግራይ ክልል ለማካለል የሕወሓት መራሹ መንግስት እርምጃ ለመውስድ በአካባቢው መገኘቱን ተከትሎ ከተማዋ በአፋር ተወላጆች ከፍተኛ ተቃውሞ እየታመሰች መሆኑን የዜና ምንጮችን ጠቅሶ ምኒልክ ሳልሳዊ ዘግቧል። እንደ ዘገባዎቹ ከሆነ ከትላንትና ቀትር ጀምሮ የተነሳው ተቃውሞ የአፋር ህዝብ በቦታው በመገኘት ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመሆን ከባድ መሳሪያ ከታጠቁ የሕወሓት ወታደሮች እና የፈደራል ፖሊስ አባላት ጋር ፊት ለፊት በመፋጠጥ መሬታችን “ከትግራይ አይቀላቀልም፤ አናስነካም” በሚል ከፍተኛ ተቃውሞ በማድረግ ላይ ነው።

ዝርዝር መረጃ እንደደረሰን እንመለሳለን።


ሞት የስብሐት ነጋ በርን እያንኳኳ ነው (ሁኔ አቢሲኒያዊ ከፒተርቦሮው ዩ.ኬ)

$
0
0

አቶ ስብሃትን ጠጋ ብለው የሚያውቁት ሰዎች “አቦይ ብላችሁ አትጥሩት። አባታዊ አንደበትና ምግባር የለውም እርሱን አቦይ ማለት ትግራይ የሽማግሌ መሀን እንደሆነች መቁጠር ነው” ይሉታል፡፡

ሰውዬው ስብሐት ነጋ የህወሓትን አመሰራረት ቅድመ ታሪክ ለሚያውቅ ሰው ምን ያህል ተንኮለኛ እና በዘር ልክፍት የተለከፈ እንደሆነ ግልጽ ይሆንለታል፡፡ በ1963 ዓ.ም እንደተመሰረተ የሚነገርለት ማገብት (ማህበር ገስገስቲ ብሔረ ትግራይ) የተመሰረተው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትግራይ ተወላጅ ተማሪዎች ነበር፡፡ የማህበሩ ተልእኮም የተለያዩ የበጐ አድራጐት ስራዎችን በክረምት ወደ ትግራይ በመሄድ ማከናወን የሚል ነበር፡፡ በሂደት ሙሉ በሙሉ ወደ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በመቀየር ለተሐህት/ህወሓት መመስረት መሰረት ሆነ ለዚህ ዓላማ የማስቀየር ስራ ትልቁን አስተዋፅኦ ካደረጉት መካከል ደግሞ ዛሬ ታሞ የሚማቅቀው ስብሐት ነጋ አንዱ ነው፡፡
ስብሐት ነጋ የህወሀትን መስመር እና ዓላማ መሀንዲስ ከመሆንም አልፎ እስከዛሬ ለብዙ ሰዎች ምስጢር በሆነ መልኩ መለስ ዜናዊንም ወደ ህወሀት ሊቀመንበርነት ብሎም የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስተር ያደረገ እና በህወሀት ክፍፍል ወቅትም ትልቅ ሚና ከነበራቸው ቀደምት የህወሀት ታጋዮች አንዱ ነው፡፡

ለባለፉት 23 ዓመታት የኢትዮጵያን ህዝብ ከጀርባ ሆነው ሲያንቀጠቅጥ የነበረው አይተ ስብሐት ነጋ እርሱም ተራው ደርሶ ቤልጅየም ብራሰልስ በሚገኘው ሴንት ሚካኤል ሆስፒታል Hôpital Saint Michel – (Brussels) መመላስ ከጀመረ 11 ዓመታት እንደሞላው የውስጥ አዋቂዎች ቢገልፁም የበሽታው አይነትና የሰውዬው የጤንነት ሁኔታ እስካሁን ድረስ ከቅርብ ሰዎች ውጪ ሳይወጣ ቀርቷል ሆኖም የህወሀት የውስጥ ሹኩቻን ተከትሎ ሚስጥሮ እያፈተለኩ መውጣታቸውን ቀጥለው ዛሬ ስለ ስብሀት ነጋ ጤንነት በተመለከተ ለዚህ ጽሁፍ ፀሀፊ አፈትላኪ መልዕክት ደርሷል፡፡

ከታማኝ ምንጮች የተገኙት መረጃዎች እንደሚያሳዩት ሰውዬው ማለትም ስብሐት ነጋ brainstem glioma በተባለ የካንሰር አይነት መጠቃቱን ገልፀዋል፡፡ ይህ የካንሰር አይነት በብዛት በህፃናት ላይ የሚታይ ሲሆን በአዋቂዎች ዘንድ ግን በዚህ የካንሰር ዓይነት የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከ100,000 አንድ እንደሆነ የሳይንስ ማስረጃዎች ያሳያሉ፡፡

Brainstem glioma ስለተባለው የካንሰር አይነት መንስዔ እስካሁን የህክምና ባለሙያዎች ምንም ያሉት ነገር ባይኖርም በካንሰሩ የተጠቃ ሰው ግን ከፍተኛ የሆነ የራስ ህመም፣ ራስን የመቆጣጠር እና የማስመለስ ችግር እንደሚያጋጥመው ያስረዳሉ፡፡

በዚህ ካንሰር ተጠቅተው ወደ ህክምና ከሄዱ ሰዎች መካከል 37% የመኖሪያ እድሜያቸው ቢበዛ ዓንድ ዓመት 20% ያህሉ ሁለት ዓመት 13% ቢበዛ ቢበዛ ከሶስት አመት በላይ በህይወት የመኖር እድላቸው አነስተኛ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

ከህወሀት አፈትልኮ የወጣው መረጃ እንደሚያሳየው ስብሐት ነጋ ባለፉት 11 ዓመታት ቤልጂየም ሲመላለስ የነበረው በዚሁ የካንሰር ምክንያት እንዳልነበረ እና የዚህ አይነት የካንሰር ተጠቂ እንደሆነ የተነገረው ፌብራዋሪ 9 እለተ እሁድ ቀን እንደነበር ጨምረው ገልፀዋል፡፡
Sbehat_Nega
የአቶ ስብሐት ነጋን መታመም ተከትሎ በሰውዬው ላይ በየዕለቱ የተለያየ ባህሪ እንደሚመለከቱ ገልፀው በተደጋጋሚ ከተለያዩ ስብሰባዎች ላይ አቋርጠው እየሄዱ እንደሚገኙ አክለው ገልፀዋል፡፡

በጦርነቱ ዘመን የትግራይ ህዝብ እጅግ የከፋ ድርቅና ረሀብ ሲፈራረቅበት፤ ከመሀል አገር የእርዳታ እህል እንዳይደርሰው መንገድ በመዝጋት፤ እነሱ በተቆጣጠሩት አካባቢና ባልተቆጣጠሩትም አካባቢ “እኛ ነን ለህዝባችን ረድኤት ድርጅቶች የሚያቀርቡትን እርዳታ ማደል ያለብን” ብለው የተባበሩት መንግስታትን ግራ አጋብተው ለረሀብተኛው እንዲያከፋፍሉ መድሀኒትና ምግብ ይሰጣቸው የነበሩ ሲሆን ያንን በብዙ ሚሊዮን የሚገመት የእርዳታ እህልና ቁሳቁስ ከአረብ ነጋዴዎች ጋር በመመሳጠር በቀጥታ ባህር እያሻገሩ በመሸጥ፤ በኩንታሎች አሸዋ እየሞሉ ለጋሾችን በማታለል እንዲገዙአቸው በማድረግ፤ በሚሊዮን ዶላር ሲንበሸበሹ፤ የጦር መሳሪያ ሲሸምቱ፤ የትግራይ ህዝብ እንደቅጠል ይረግፍ ነበር። እነሱ በየጫካው ከሰራዊቱ እየተሸሸጉ አረቄ ጠግበው ከውሽሞቻቸው ጋር ከበሮ እየደለቁ እየጨፈሩ ይዳሩ እንደነበር ህወሀትን ጥለው የኮበለሉ የቀድሞ አባላቶች የሚገልፁ ሲሆን ለእነዚህ ሁሉ ግፍ እና በደል መፈፀም ከፍተኛ ሚና የነበራቸው እኚሁ የካንሰር ተጠቂ ነበሩ፡፡

ሞት ፍትሃዊ ነው በቅርቡ እንኳን አፈ ቀላጤ መለስ ዜናዊን ከህወሀት አለማየው አቶምሳን ከኦህዴድ ( ኦህዴድ ብዬ ስጠራው የዋሸው ይመስለኛል) የወሰደ ሲሆን አሁን አፉን ከፍቶ ከስብሐት ነጋ ደጃፍ ደርሷል ስብሀት ነጋም ሞትን ወደ ቤቱ ላለማስገባት ከአዲስ አበባ ወደ ብራሰልስ በየዕለቱ እየተመላለሰ ይገኛል ግና ሞትን ሸሽቶ እስከመቼ ሊደበቅ እስከ አንድ ወር ወይስ?

የአባ መላ (ብርሃኑ ዳምጤ) መገለባበጥና ኢሳት

$
0
0

ከእንደልቡ/ዳግም (ከቫንኮቨር፣ ካናዳ)

አባ መላ ማን ነው?

በቅጽል ስሙ “አባ መላ” በእውነተኛ ስሙ ደግሞ ብርሃኑ ዳምጤ ተብሎ ይጠራል፣ በ60ዎቹ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ አዛውንት ነው (ምንም እንኳ ስራው እንደ እድሜው ባይሆንም)። ፓልቶክ የሚባለውን የማህበራዊ መገናኛ መድረክ በመጠቀም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዲስኩር በማሰማት ይታወቃል። በወጣትነቱ ኢህአፓ ውስጥ ነበር የሚባለው ብርሃኑ ዳምጤ ወዲያውም የኢህአፓን መዳከም አይቶ ወደ ደርግ ቡድን መቀላቀሉን የሚያውቁት ይናገራሉ። በወቅቱ አብረውት በኢህአፓ ውስጥ ይሳተፉ የነበሩ ወጣቶችን ለደርግ በእጅ መንሻ መልክ አሳልፎ ሳይሰጥ እንዳልቀረ በደርግ ካድሬነት ቆይታው የሚያውቁት ይጠረጥራሉ አንዳንዶች ደግሞ አፋቸውን ሞልተው ይናገሩታል።
aba-mela-esat
ብርሃኑ ዳምጤ ከደርግ መውደቅ በኋላ በስደቱ ዓለም (ዳያስፖራ) ፖለቲካ መድረክ ብቅ ያለው በምርጫ 97 ወቅት የዝነኛውን ቅንጅት ማልያ ለብሶ ነበር። ይሁንና በስልጣን ላይ ያለው የህወሃት/ወያኔ መንግስት ምርጫውን አጭበርብሮ፣ የምርጫውን መጭበርበር የተቃወሙትን በገፍ በአደባባይ በጥይት ደብድቦ፣ ህዝቡ የመረጣቸውን የቅንጅት አመራሮች፣ ጋዜጠኞችና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን ጨመሮ ከ50 ሺህ በላይ ባብዛኛው ወጣቶችን አስሮና በየጦር ካምፖቹ አጉሮ በአምባገነንነቱ ለመቀጠል ሲወስን ብርሃኑ ዳምጤም ባፋጣኝ የቅንጅትን ማልያ አውልቆ የህወሃት/ኢህአዴግን ማልያ ለብሶ ቁጭ አለ።

ሰሞኑን ደግሞ ብርሃኑ ዳምጤ አስደናቂ መገለባበጥን ፈጽሞ የህዝብን አይን አስበልጥጧል። እነዚህ ብርሃኑ ዳምጤ (አባ መላ) ሰሞኑን የሚፈጽማቸው መገለባበጦች በ1960ዎቹ እና 70ዎቹ ከነበሩት የመገለባበጥ ትሪኢቶቹ ለየት የሚያደርጋቸው ነገር ቢኖር አሁን መገለባበጡን የሚፈጽመው በቀጥታ ስርጭት ወቅት (በፓልቶክ) መሆኑና ጉዳዮን በመሪ ዜና መልክ የሚዘግብለት የቴሌቪዥን ጣብያ “ኢሳትን” ማግኘቱ ነው።

ብርሃኑ ዳምጤ ከጥቂት ወራቶች በፊት ነበር የተሰለፈበት የህወሃት/ኢህአዴግ ጎራ በተለይም ከወያኔው ቁንጮ መለስ ዜናዊ ሞት በኋላ እየተዳከመ መምጣትን አይቶና ገምቶ ወያኔዎችን “አፍንጫችሁን ላሱ፣ እኔ ከአሁን ብኋላ የድሮው አባ መላ አይደለሁም፣ እንዲያውም ጉዳችሁን አዝረጠርጣለሁ…” በማለት ፉከራ ቢጤ አሰምቶ የዲሞክራሲና የነጻነት ታጋዮችን ጎራ መቀላቀሉን ያበሰረው።

መንፈቅ እንኳ ሳይሞላ አባ መላ በመጣበት አይነት መንገድ ተመልሶ ህወሃት/ኢህአዴግን ለማገልገል መወሰኑን ይፋ አደርጓል። ለሱ እምብዛም አዲስ ያልሆነውን የክህደት ቁልቁለትም ዳግም ተያይዞታል።

አባ መላ፣ ኢሳትና ዳያስፖራው

የኢሳት ጋዜጠኞች፣ አንዳንድ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና የተቃዋሚ ፖለቲከኞችም ጭምር ይህ አባ መላ የሚባለውን ቦታ እየቀያየረ ይሚጫወት ዝቅተኛ ካድሬ ከሚገባው በላይ ቦታ ሰጥተውት እንደነበር እገምታለሁ፣ በውጤቱም ተከታዮቻቸውን ያሳሳቱና ያዘናጉ ይመስለኛል። ይህንን ጉዳይ ማንሳቴ “ብዬ ነበር” ለማለት ሳይሆን ይልቁኑም ይህ ክስተት እንደ መማሪያ ሆኖ እንዲያልፍ በመፈልጌ መሆኑን አባብያን እንዲረዱልኝ እፈልጋለሁ።

እንደ አባ መላ አይነቱ ቀደም ሲል በተደጋጋሚ የመገለባበጥ ብቃቱን ያሳየ ወለፈንዴ ተቃዋሚ ጎራ ገብቻለሁ ሲል አያያዛችን ጥንቃቄ የተሞላበት፣ ሊሆን ይገባል። በቅርቡ ተገልብጦ ሊያሳፍረን ይችላል ብሎ መስጋት፣ ለጉዳዩ መጠነኛ የአየር ሰዓት መስጠትና ውሎ አድሮ ደግሞ መርጋቱን እያዩ ወደሌላው መተላለፍ ተገቢ ነው። እንደው በአንድ ጊዜ ይህን ከምላስ በስተቀር ቁም ነገር የሌለው ተራ ካድሬ ወደላይ ቆልሎ አንድ ጊዜ “አክቲቪስት” ሌላ ጊዜ ደግሞ “የፖለቲካ ተንታኝ” እያሉ በኢትዮጵያውያን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ የተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅትን እንዲመራ ማጨት ድረስ መጓዙና አሉ ከሚባሉ ፖለቲከኞች ጋር መድረክ እንዲጋራ ሁኔታዎችን ማመቻቸቱ አገባብ አልነበረም።

የኢሳት ባልደረባ ደረጀ ሃብተወልድ የአባ መላን መገልበጥ አስመልክቶ በፌስቡክ ገጹ ላይ እንዳሰፈረው ከሆነ ግን ኢሳቶች ከስህተቶቻቸው ሊማሩ የተሰናዱ አይመስልም ይልቁኑም አባ መላን አስመልክቶ ሊቀርቡ የሚችሉ ትችቶችን ቀድሞ ለመከላከል ነው ሙከራ የሚያደርጉ ያሉት። ደረጀ ሃብተወልድ እንዲህ ነበር ያለው፣

“ነገሩ ወዲህ ነው። አባ መላ ኢህአዴጎችን እየሰደበ ወደ ተቃዋሚው ጎራ ሲቀላቀል “አገኛለሁ” ብሎ ያሰላው ጥቅም ነበር። ሆኖም ሀሳብን በነፃነት ለመግለጽ ከሚያስችል ነፃ መድረክ ውጪ ሌላ ነገር ሊያገኝ አልቻለም። ባገኘው ነፃ መድረክም ማንም ሳይቆነጥጠው ከትንሽ እስከ ትልቅ የቀድሞ አለቆቹን እስከ ዶቃ ማሰሪያቸው ነግሯቸዋል። እኛንም አስቆናል። ስንስቅለት ጨምሮ ጨማምሮ አቅምሷቸዋል። እኛም፦“የአገሩን ሰርዶ ባገሩ በሬ” እያልን ተዝናንተናል። ከዚያ ባለፈ ግን ለቁም ነገር ያሰበው ሰው ስለመኖሩ እጠራጠራለሁ።”

የደረጀን አባባል ሁሉም ሰው የተቀበለው አይመስልም ይህን ለማሳየት ከተቃውሞ ሃሳቦች መካከል አንዱን ከዚያው ከደረጀ ሃብተወልድ የፌስቡክ ገጽ ልበደር፣

“የአባ መላን መገልበጥ ተከትሎ ኢሳቶች ከተወቃሽነት ለመዳን የዘየዳችሁት ይሄው ነው? ደረጀ “አባ መላን ለቁም ነገር ያሰበው ያለ አይመስለኝም” ያልከው ፈጽሞ ከእውነት የራቀ ነው፣ በሳውዲ ወገኖቻችንን ለመታደግ በተቋቋመው አለም አቀፍ ድርጅት ውስጥ ከታማኝ እና አበበ ገላው ቀጥሎ ሶስተኛ ሰው ተደርጎ አልነበረም? በጣም ብዙ ማለት ይቻላል… “እጄን በጄ” ሆኖብን እንጂ። ለማንኛውም ከስህተቶቻችሁ ተማሩ፣ በጣምም አንፍጠጥ ያስተዛዝባል።” Ethiopian Unity

ለማጠቃለል ያህል የሚሰራ ጋዜጠኛ፣ ለውጥ ለማምጣት የሚተጋ ፖለቲከኛና የዲሞክራሲ ታጋይ በሂደት ውስጥ ስህተት ሊሰራ ይችላል፣ ከስህተቶች ትምህርት ወስዶ ለሁለተኛ ጊዜ ተመሳሳይ ስህተትን ላለመድገም ጥረት ማድረግ ግን ሊለመድ ይገባል። ነገሮቻችን ሁሉ “ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ” እንዳይሆኑ ሃላፊነት ወስደን ከስህተቶቻችን ለመማር ዝግጁ እንሁን።

የሀገራችንን ድንበር ለሱዳን መስጠቱን እንደሚቃወሙ በፊርማዎ ያስመዝግቡ

$
0
0

meles cartoon
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት በገዥው ህውሀት/ኢህአዴግ እና በሱዳን መንግስት መካከል እየተካሄደ ያለውን ሴራ እንቃወማለን፡፡

ይህ ሴራ የሚካሄደው ህዝብን በማይወክል ጠባብ ቡድን በመሆኑ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጀርባ የሚፈጸመውን ማንኛውንም ውል እንደማንቀበል ካሁኑ እንዲታወቅልን ለተባበሩት መንግስታት፣ ለአፍሪካ ህብረት እና ለሌሎችም አለም አቀፍ ድርጅቶችና መሪወች የሚቀርብ የተቃውሞ ፊርማ በማሰባሰብ ላይ እንገኛለን።

እርስም ስዎን በማስፈር የዚሁ ታሪካዊ እንቅስቃሴ አካል እንዲሆኑ በትህትና እንጠይቃለን። የናት ሀገራችን ኢትዮጵያ ዳር ድንበር ሲደፈር ሁሉም የሚችለውን ማድረግ ሀገራዊ ግዴታው ነው።

ለመፈረም የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ

http://www.ipetitions.com/petition/stop-secret-border-deal-between-ethiopia-and-Sudan

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

[የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ጉዳይ] –ማን ለጠበቃ ፈረመ???

$
0
0

ሰላም ለሁላችሁ፤
debereselam Minnesota
ለሰላም እና ለአንድነት ከቆሙ ምዕመናን የተላለፈ መልዕክት፦

በቤተክርስቲያናችን መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ቤተክርስቲያኑን ወክሎ ማንኛውንም ውለታ/ሰነድ መፈረም የሚችለው ሊቀመንበሩ ብቻ እንደሆነ በግልጽ ተቀምጧል። የእየአንዳንዱ የቦርድ አባል የሥራ ድርሻ በተዘረዘረበት አንቀጽ 6 ላይ ማን በቤተክርስቲያኑ ስም ሰነዶችን
መፈረም እንደሚችል ተደንግጎ እናገኛለን ። አንቀጽ 6 ክፍል 3 ሀ ተ.ቁ 7 እንዲህ ይላል፦

“ሊቀመንበሩ፦

7. ጠቅላላ ጉባኤው፤ የባለአደራዎች ቦርድና የሥራ አስፈጻሚው ኮሚቴ የተስማሙባቸውን ሰነዶችና ስምምነቶች ቤተክርስቲያኒቱን በመከወከል ይፈርማል”

ቤተክርስቲያኑን ወክያለሁ የምትለው ይህች ጠበቃ ግን ገና ሊቀመንበሩ በቦርድ ሕገወጥ ስብሰባ ታግደዋል ሳይባል ነው የቤተክርስቲያኑ ጠበቃ ነኝ ያለችው። ይህም ለሕጋዊው ሊቀመንበር በማያገባት ገብታ የሕዝብ ተምራጭ የሆኑትን ሊቀመንበር ከቦርድ ተባረዋል ብላ በጻፈችው ደብዳቤ ተጠቅሷል። እነርሱ ሊቀመንበር ያሉት እኛ ግን በሊቀመንበርነት የማናውቀው ሰውም ይህን ሰነድ የመፈረም ስልጣን የለውም። እነርሱም መርጠነዋል ያሉት ከዛ በሗል ነው። እናም የማርች 9ኙ ቤተክርስቲያኑ ተከሰሰ አዋጅ አጣብቂኝ ውስጥ የመግባታቸው ውጤት ነው። ድሮም ወያኔ ወንዝ አያሻግርም።
የእምነት ሕፀጽ የሌለባትን ቤተክርስቲያን በጥብጠው፣ ሲካፈሉት የኖሩትን ቅዱስ አገልግሎት እንደ መርገም ቆጥረው ቀኖና ያጎደለ ቤተክርስቲያን ነው ሲሉ የማይሰቀጥጣቸው፣ ሕዝቡን በማሸበር የፖለቲካ ተልእኳቸው ተከታይ የሚሆን መስሏቸው የሌለውን ችግር ፈጥረው ሰላማችንን ሲያምሱ መክረማቸውን
ያየ መድኃኔዓለም ቤቱን ባጸዳበት ቀን እነዚህንም ሊያጸዳ እያጻፋ አናገራቸው። በጥፋት ላይ ጥፋት በክስረት ላይ ክስረት ብቻ ስለሆነ ትርፉ እባካችሁ የበደላችሁትን ጌታ አና ኅዝብ ይቅርታ ጠይቃችሁ አርፋችሁ ተቀመጡ። የባሰ ሳይመጣ። ጊዜው ለዚህ የተመቸ ነውና።

ይህ ሕዝብ ሳይፈቅድና ሳያምንበት በቤተክርሲታኑ አቋም ላይ አንዳች ለውጥ አይመጣም!!! አሁንም ወደፊትም በአባቶች መካከል ያለው መለያየት እስኪወገድ ድረስ ከቤተክርስቲያናችን ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ሳይሆን ከስልጣን ሽኩቻ፣ በዘረኝነትና በሙስና ከተጨማለቀ አስተዳደር ገለልተኛ ነን !!! ወዳጆቼ የአስተሳሰብ ልዩነት እኮ እንዲህ በግትረኝነትና ለምን ፍርስርስ አይልም እያሉ የሚያራምዱት አይደለም። ሕዝብ ወሰነ። እናንተ ግን 40/50 ሰው ጎድሎ ነበርና በክፍተኛ ድምጽ የተወሰነውን ውሳኔ አንቀበልም ብላችሁ በማያዋጣ ጎዳና መጓዝ ጀመራችሁ። መጨረሻችሁም ይኽው ከፍተኛ ወጪ አስከተለ። አሁንም አስቡበት አያዋጣችሁም። ሽንፈትን መቀበል ከባድ ቢሆንም ሊመጣ ካለው ከባድ ሽንፈት ይሻላልና ክርስቲያን ከሆናችሁ ይብቃችሁ። ባስቸኳይ ኅዝቡ ባቀረበው አጀንዳ መሠረት ጠቅላላ ጉባኔ ጥሩ። ሕዝቡ ከፈለገ ትቀጥላላችሁ ካልፈለጋችሁ ደግሞ እንደመረጣችሁ ያወርዳችኋል።
እስኪ እንደ ክርስቲያን ይቅርና እንደሰው ለደቂቃ አስቡት? በዚህ ባመጣችሁት ጉዳይ ምክንያት ምን ተጠቀምን? ምን አተረፍን? ችግር ተፈታ? ተቃለለ? ወይንስ ተባባሰ? ገለልተኝነት ቀረ? የችግሩ ምንጭ ፖለቲካ ነው። ችግሩ የሚፈታውም ፖለቲካው የሆነ ለውጥ ሲያመጣ ነው ወይንም ሲለወጥ ነው። ማንም ቢዳክር የተለያዩት አባቶች ሳይስማሙ/ሳይታረቁ ይህ ችግር አይፈታም!!!

በደብራችን በደብረሰላምም ሆነ በተዋሕዶ እምነታችን ላይ ምንም ከወትሮው የተለየ የእምነት ችግር የለም!!! ችግሩ የአስተዳደርና የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ነው። የእምነት ችግር አለ ለሚል ሰው ግን እስካሁን በገለልተኛ ቢተክርስቲያናት የተካፈለውን መንፈሳዊ አገልግሎት ምን ሊያደርገው ነው? ንሰሐ ሊገባበት ነው? ከዚህ በኋላስ በገለልተኛ ቤተክርስቲያን ይገለገላል? በርግጥ ያየበት መነጽር ስሕተት እንደነበረ ካመነ ምንም አይደል። አለበለዚያግን ክርስትናው አጠያያቂ ነው። ለማንኛውም መድኃኔዓለም ልቦና ይስጣችሁ። እውነት የቤተክርስቲያን ነገር ካሳሰባችሁ ብዙ የሚሰራ ሥራ አልና እዛላይ ብንሰራ ይሻላል። እናም እባካችሁ ይብቃችሁ!!!

የአውሮፓ ሕብረት በአዲስ አበባ መንግስትን እና ተቃዋሚዎችን እያነጋገረ ነው

$
0
0

የፖለቲካ ምህዳር መስፋት፣ የ2007 ምርጫ፣ የታሳሪዎች ጉዳይ በአጀንዳነት ተነስቷል

ከዘሪሁን ሙሉጌታ

በአውሮፓ ኅብረት የአፍሪካና የኢትዮጵያ ቋሚ አምባሳደር የኢትዮጵያ መንግስትንና የተቃዋሚ ፓርቲዎችን እያነጋገረ ነው። የኅብረቱ ቋሚ አምባሳደር አማካኝነት መካሄድ የጀመረው ውይይት በሀገሪቱ የፖለቲካ መህዳር መስፋት፣ በ2007ቱ ምርጫ፣ ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ የታሰሩ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች እንዲሁም በሀገሪቱ ስላለው የሰብአዊና የዴሞክራሲ መብቶች ዙርያ መሆኑ ታውቋል።
au addis ababa
ባለፈው ዓመት የኅብረቱ ቋሚ አምባሳደር በመሆን የተሾሙት አምባሳደር ቻንታል ሔብሪች ኅብረቱን በመወከል በኢትዮጵያ ውስጥ የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች የበለጠ የሚከበሩበትን ገንቢ አማራጭ እያፈላለጉ ነው። በዚህም የአምባሳደሯ እንቅስቃሴ መሠረት የካቲት 26 ቀን 2006 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በመገኘት ከሌሎች የአውሮፓ ሀገራት አምባሳደሮች ጋር በመሆን በሀገሪቱ አጠቃላይ የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ዙሪያ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ውይይት አካሂደዋል። አምባሳደሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ውይይት ካካሄዱ ከአምስት ቀናት በኋላ በሀገሪቱ ካሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አንዱ ከሆነው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አመራር አባላት ጋር በጽ/ቤታቸው ውይይት አካሂደዋል።

በአውሮፓ ኅብረት የአፍሪካና የኢትዮጵያ አምባሳደር ቻንታል ሔብሪች ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ጋር በተወያዩበት ወቅት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩ ዴሞክራሲያዊ ሕጋዊ መሠረት የተከተለ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ላይ ቢሆንም፤ የበለጠ መሻሻል በሚገባቸው ቀሪ ስራዎች መወያየታቸው መዘገቡ ይታወሳል። በተጨማሪም በመጪው ዓመት የሚካሄደው ብሔራዊ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ በሚሆንበት ጉዳይ ላይ መወያየታቸው አይዘነጋም።

በተመሳሳይ ባለፈው ሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2006 ዓ.ም በአውሮፓ ኅብረት ጽ/ቤት የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራውና የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ከኅብረቱ አምባሳደር ቻንታል ሔብሪች እንዲሁም በአውሮፓ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድና የህንድ ውቅያኖስ ክፍል ኃላፊ ጋር ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱም በአጠቃላይ ፓርቲው እያደረገ ስላለው እንቅስቃሴና “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚለው የፓርቲው ክፍል ሁለት ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ላይ ማብራሪያ መጠየቃቸውን፣ የገዢው ፓርቲ የመሬት ፖሊሲ በሀገሪቱ መሬት የጥያቄ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ጥያቄ በመሆኑ በጥቅሉ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ጤናማ እንዳይሆንና መንግስታዊ የሙስና ሥርዓት እንዲጎለብት መደረጉን አርሦ አደሩም ከድህነት እንዳይወጣ በማድረግ ዋነኛ የዴሞክራሲ ማፈኛ መሆኑን ማስረዳታቸውን በውይይቱ የተሳተፉት አቶ ሀብታሙ አያሌው ለሰንደቅ ጋዜጣ ገልፀዋል።

ከዚህ ጎን ለጎን በእስር ስለሚገኙ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች የፓርቲው አመራሮችን በተመለከተ ማብራሪያ መስጠታቸውን፣ አቶ አስራት ጣሴ ስለታሰሩበት ምክንያት፣ ምርጫ 2007 ላይ ፓርቲው ስላለው አቋም፣ በኢትዮጵያ የመብት ጥሰቱ በምን ደረጃ ላይ እንዳለና በስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርት፣ የሚዲያ ሞኖፖሊና የግል ፕሬሱ ወዳከም ጋር የተያያዙ ችግሮች ዙሪያ ውይይት ማካሄዱን ከአቶ ሀብታሙ ገለፃ መረዳት ተችሏል።

በመጪው ሚያዚያ ወር ብራስልስ ላይ የአውሮፓ ኅብረትና የአፍሪካ ኅብረት በሚያካሂዱት የግራ ስብሰባ ላይ የአንድነት ፓርቲ ተወካይ ተገኝቶ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ ላይ ንግግር እንዲያደርግ ጥያቄ መቅረቡንም አቶ ሀብታሙ አያይዘው ገልፀዋል።

የአውሮፓ ኅብረት በገዢው ፓርቲ እና በተቃዋሚዎች መካከል ገንቢ ውይይት ተደርጎ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱ ከፍ ማድረግ አለበት ያሉት አቶ ሀብታሙ፣ ይህ ካልሆነ ግን በምስራቅ አፍሪካ አደገኛ ወደሆነ የፖለቲካ አለመረጋጋት ሊፈጠር እንደሚችል ገልፀዋል።

የአውሮፓ ኅብረት ከተለያዩ ሀገራት ጋር ሰፊ የልማት፣ የቴክኒክ ድጋፎች እንደሚያደርግ ይታወቃል። በምትኩ ሀገራቱ የዜጎቻቸውን ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲያከብሩ ከፍተኛ ግፊት ያደርጋል። ኢትዮጵያም የሎሜ ኮንቬንሽንን እ.ኤ.አ በ1975 ዓ.ም ከፈረመች ጊዜ አንስቶ ከኅብረቱ ጋር የልማት ትብብር መስርታለች፤ ኅብረቱም በአውሮፓ የልማት ፈንድ (European Development Fund) (EDF) እገዛ ያደርጋል። በተለይ በትራንስፖርት፣ በገጠር ልማት፣ ባልተማከለ የማኅበራዊ አገልግሎት ድጋፍ፣ በንግድ፣ በጾታ በሰብአዊ እርዳታ ድጋፍ እና በአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ላይ ሀገሪቱን ይደግፋል። የድጋፍ መጠኑም በቅርቡም ወደ 600 ሚሊዬን ፓውንድ ይደርሳል።

አዲሲቷ የኅብረቱ ቋሚ አምባሳደር በመንግስትና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል የተካረረውን ግንኙነት በማለዘብና ወደ ገንቢ ውይይት እንዲመጡ ማበረታታታቸው በበጎ ዓይን እየታየላቸው ነው። አምባሳደር ቻንታል ባለፈው ዓመት የሹመት ደብዳቤአቸውን ከማስገባታቸው በፊት በአውሮፓዊቷ ኪርጊስታን ሀገር የኅብረቱ ቋሚ አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል። የቤልጂየም ተወላጅ የሆኑት አምባሳደር ቻንታል በኢትዮጵያ የኅብረቱ ቋሚ አምባሳደር የነበሩትና ባለፈው ግንቦት ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን የሀገራቸውን ልጅ አምባሳደር ቫቪየር ማርሻልን ተክተው ወደ ኢትዮጰያ መምጣታቸው ይታወሳል።

(ዜናው የተገኘው ዛሬ በአዲስ አበባ ከታተመው ሰንደቅ ጋዜጣ ነው)

ስለሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ አመሠራረትና አሁን ያለበት ሁኔታ ምናልባት እስካሁን ያልሰማናቸው ጉዳዮች – (ልዩ ጥንቅር ከኢትዮጵያ ድምጽ ራድዮ)

$
0
0

debereselam Minnesota
“ቦርዱ በአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ ምእመናኑን ሰብስቦ ምእመናኑን ምንድን ነው የምትፈልጉት ሊለው ይገባል” – አጥናፉ
“ቤተክርስቲያኑ ሲመሰረት፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሴ በቋንቋችን ሥሰማ በደስታ ብዛት አልቅሻለሁ” ሰዊት
“ቤተክርስቲያኑ ገለልተኛ ነው ተብዬ አምኜበት ነው የገባሁት፤ ሃገር ቤት ይግባ የምል ከሆነ ጥዬ መውጣት እንጂ አሁን ተነስቼ ልበጥብጥ ማለት አይገባም ” – አበራ
“ሁሉንም ወገኖች ለማነጋገር እንፈልጋለን” አህመድ


የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ እስካሁን የተረጋጋ ሁኔታ የለም። ይህን ተከትሎ ከሚኒሶታ አልፎ በመላው ዓለም መነጋጋሪያ የሆነ ጉዳይ ሆኗል። በርካታ ሕዝብ፣ የኢትዮጵያ ኮምዩኒቲን ጨምሮ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ ሕዝብ የቤተክርስቲያኑን ቀጣይ እጣ ፈንታ እንዲወስን ቢጠይቁም ቦርዱ እስካሁን ምላሽ የሰጠው ምላሽ አለመኖሩ አነጋጋሪ ሆኗል። አባቶችም ሁለቱንም ወገኖች ለማስማማት ጥረት አላደረጉም በሚል በም እመናኑ ወቀሳ እየደረሰባቸው ይገኛል። ይህ እንዳለ ሆኖ በሚኒሶታ ዘወትር እሁድ የሚሰራጨው የኢትዮጵያ ድምጽ ራድዮ በዚህ ትልቅ ቤተክርስቲያን ዙሪያ ሰፊ ዘገባ አቅርቧል። ምናልባት እስካሁን ሰምተናቸው የማናውቃቸው ጉዳዮች ተነስተዋል። ብታደምጡት ትጠቀማላችሁ ብለን እናስባለን።

የብርሃኑ ዳምጤ (አባመላ) ቅልቅል (ከክንፉ አሰፋ) ጋዜጠኛ

$
0
0

ብርሃኑ ዳምጤ እንደገና ሲገለበጥ የአስር አመት ልጅ ሳለሁ ያጋጠመኝን አንድ ክስተት አስታወሰኝ። በሰፈራችን ውስጥ ልጆችን ሁሉ የሚጠሉ አንድ ሰውየ ነበሩ። አንድ ቀን በድንገት ተነሱና የሰፈሩን ሰው ሁሉ መሰናበት ጀመሩ። በእጃቸው 3 ሜትር የሚያህል ርዝመት ያለው ገመድ ይዘዋል። “የሰፈሩ ልጆች ስላስቸገሩኝ ራሴን ልስቅል ነው። ደህና ሁኑ…” እያሉ ሁሉንም ተሰናብተው ሲያበቁ ለመሰቀል መንገዳቸውን ጀመሩ። የእኝህ ሰው ውሳኔ ለመንደሩ ሰው ሁሉ ደንታ አልሰጠውም።

የሰፈር ልጆች ግን ተከተልናቸው። ብዙ ነበርን። ሰውየው ተራራ ሲወጡ አብረን ወጣን። ቁልቁል ሲወርዱም አብረን ወረድን። ጉዞው አሰልቺ ነበር። ግን ተስፋ ሳንቆርጥ ጉዱን ለማየት ስንል ተከተልናቸው። በመጨረሻ አንድ ዛፍ አገኙና የሚሰቀሉበትን ገመድ እዛፉ ላይ ማሰር ጀመሩ።

ሰው ሲሞት አይተን ስለማናውቅ ሁኔታውን እንደ ልብ አንጠልጣይ ፊልም ነበር በጉጉት የምንከታተለው። ሰውዬው በዚህ ሁኔታ ለመሞት መወሰናቸው ብዙም አላስደነገጠንም። ይልቁንም ከኛ እየቀሙ በግቢያቸው ያጠራቅሙዋቸው ኳሶቻችን ነጻ ሊወጡልን ነው ብለን ተደስተናል።

ገመዱን አስረው ራሳቸውን ለመሰቀል ካመቻቹ በኋላ ዘውር ብለው እኛን ተመለከቱን። «እባኮን ይተው!» የሚላቸው አንድ እንኳን ሰው አልነበረም። ለደቂቃዎች በአትኩሮት ከተመለከቱን በኋላ እንዲህ አሉ። «እንዲያውም ደስ አይበላችሁ። ሃሳቤን ቀይሬአለሁ። አልሰቀልም!»

ዛፉ ላይ ያሰሩትን ገመድ ፈቱትና ወደ ሰፈር አቀኑ። ካልተሳከው የጎልጎታ መሰውያ ሲመለሱ እመንገድ ላይ ያገኛቸው አንድ ሰው ሲመክራቸው ሰማን። «ሌላ ግዜ መሰቀል ከፈለጉ ለሰው አይናገሩ። ድምጽ አጥፍተው ለብቻዎ ያርጉት። የዚህ ሰፈር ልጆች አብዝተውታል። ሰው በሰላም እንኳን እንዳይሞት እያደረጉ ነው።»
aba mela
ሰውየው ለመካሪያቸው ምንም ምልስ አልሰጡም- ግን ወደኛ እየተገላመጡ «እርሱት። አታገኙዋትም!» የማለት አይነት በአይናቸው እየዛቱብን እቤታቸው ገቡ።

ከልጅ ጋር የሚጫወቱት እንቁልልጬ መሆኑ ነው። ለዚያማ ማን አክሎን። የባሰ እልህ ውስጥ አስገቡን። … በመጨረሻ ብቻቸውን መንገድ ላይ እያወሩ መሄድ ሲጀምሩ ተውናቸው። …

የሳይበሩ አንበሳ የመታጠፉ ፍጥነት ሳይገርመን የድጋሚ ቅልቅሉን በከአዲስ ዜማ አከለበት። “እንደውም ደስ አይበላችሁ። ወያኔን ተቀላቅያለሁ!” የሚል ዜማ። የልጅነት እንቁልልጬ ጨዋታ ይመስላል። ለመዞርማ ምድርም ብርሃንና ጨለማን ለማፈራረቅ በራስዋ ዛቢያ ላይ ትዞራለች። የኋላውን ለማየት ሲል አንገትም ይዞራል። ብረትም ይዞራል – በእሳት ሲፈተን። … ቆርቆሮ ግን እንዲሁ ይጠመዘዛል።

«..እኔ እንኳን ትንሽ መቆየት ፈልጌ ነበር።» አለ ኦቦ ዳምጤ፤ ለሁለተኛው ዙር ከወያኔ ጋር ያደረገውን ቅልቅል ሲያበስር። ይህችን አነጋገር የተጠቀመባት ያለ ምክንያት አልነበረም። ወደዚህኛው ጎራ የገባው የጥምር ሰላይ (double agent) ስራ ለመስራት እንደሆነ ለማስመሰል መሞከሩ ነበር። ፈረንጆቹ (match fixing) ማች ፊክሲንግ የሚሉት በእግር ኳስ አለም ውስጥ ለተቃራኒው ተገዝቶ የመስራት ውስልትና አይነት መሆኑ ነው። እንዲህ የተራቀቀ ቢሆንማ ኖሮ እናደንቀው ነበር። ግና በዚያው ቃለ-ምልልስ ላጠፋው ጥፋት ይቅርታ ጠይቆ ጨዋታውን አበላሸው። ድንጋይ በትከሻው ባይሸከምም ህሊናውን ዝቅ አድርጎ ከአክራሪ ዲያስፖራ ጋር በመዋሉ በጣም ተሰምቶታት። ወያኔዎች ይቅርታ የሚላቸውን ለምን እንደሚወዱ አይገባኝም። ይቅርታ የሚጠይቋቸውን ሰዎች በጣም ሲወድዱ እንጂ ምህረት ሲያደርጉላቸው ግን አይተን አናውቅም። ታምራት ላይኔን በፓርላማ ካዋረዱት በኋላ ቀፈደዱት። ሰለሞን ተካልኝም ከይቅርታ አልፎ ከዲያስፖራው ርኩስነት ለመጽዳት ሲል አባን ጸበል እርጩኝ ብሎ ነበር – በዘፈን። መቀሌ ድረስ ሄዶ በኢህአዴግ ጸበል ቢጠመቅም፣ እነሱ ግን ቂማቸውን አልረሱም። ሁሉንም ማኖ እያስነኩ በአየር ላይ ያንሳፍፏቸዋል።

አባመላ ከነሱ ጋር ተጣልቶ ወደ ተቃውሞ ጎራ በሄደ ጊዜ ወያኔዎች አንድም ነገር አልተነፈሱም ነበር። ምክንያቱም ጸቡ የመርህ እንዳልነበር ያውቁታል። ጉዳዩ የግል ጥቅም ነው። መፍትሄውም ቀላል። በፈለጉት ግዜ እንደ ቆላ በሬ አሞሌ ጨው አልሰው እንደሚመልሱት አስቀድመው ያውቁታል።

በቃለ-ምልልሱ አባ መላ በካፒቴን ሀይለመድህን አበራ ዙርያ የተነሳውን ክርክር ሊቋቋመው እንዳልቻለ አልካደም። በክርክር ሲሸነፍ እንደመፍትሄ የወሰደው የወያኔን ጎራ መቀላቀል መሆኑም አዲስ ነገር አይደለም። ያኛው ጎራ በሃሳብ የተሸነፉ መሃይማን መሰብሰብያ ጎራ ከሆነ ሰንበትበት ብሏል።

ንግግር መቻል አንድ ነገር ነው። እየቀለዱ ሰውን ማሳቅም ቀላል ሊሆን ይችላል። በመናገር ሰዎችን ማሳመን መቻል ግን ሌላ ጉዳይ ነው። ይህ ጥበብን፣ ብስለትን እና አስተዋይነትን ይጠይቃል። በንግግር ሰዎችን ማሳመን መቻል ደግሞ ሮኬት ሳይንስ መሆንን አይጠይቅም። አንዳንዶች በትምህርት ያገኙታል። ሌሎች በማንበብ ይለወጣሉ። የህይወት ተመክሮም በራሱ ብዙ ነገር ያስተምራል። ከስህተታቸው እየተማሩ የሚበስሉ ሰዎችም ብልሆች ናቸው።

«አቶ መለስ ዜናዊ እድሜ ልካቸውን የአማራን ህዝብ ሲሳደቡ ሰንብተው፤ አንድ አማራ ሲሰድባቸው ግን ደግም ላይመለሱ አሸለቡ።» የሚል ቀልድ ሰምቼ በጣም ነበር የሳቅኩት። ነገሩ ልክ ነው። በሌላው ላይ የሚቀልዱ ሰዎች በራሳቸው ላይ ሲደርስ በቶሎ ይሰበራሉ ይባላል።

እናም በሃይለመድህን ጉዳይ «ከጽንፈኞች» ሳይስማማ በመቅረቱ የጠፋው በግ ወደ ቤቴ ተመለስኩ ነው እያለን ያለው። ይህ ሰው ግን ስንት ጊዜ ነው ከቤቱ የሚጠፋው?

ደግሞ ፍጥነቱ። የብርሃን ጉዞም እንደብርሃኑ ዳምጤ አይፈጥነም። ወደዚያኛው ጎራ ሲቀየስ የለበሰውን የዲያስፖራ ማልያ እንኳ ለመለወጥ ግዜ አልወሰደም። የቡናን ማልያ ለብሶ ለደደቢት የሚጫወት አይነት ሰው ነው የሆነው።

እንደዚህ አይነት ሰዎች ስብእናቸውን የሚሸከም አንገት ስለሌላቸው ወደግራም ሆነ ወደቀኝ፣ ወደፊትም ሆነ ወደኋላ ለመተጣጠፍ ችግር የለባቸውም። ይህ ሰው ወደ ቀኝ ታጥፎ በነበረበት ግዜ ከአንዴም ሶስቴ ደውሎ በስልክ አናግሮኝ ነበር። አቀራረቡ፣ አነጋገሩና ጨዋታው ያራዳ ልጅ ይመስላል። ተግባሩ ግን የአራዳ ልጅ አይደለም። ያራዳ ልጅ ባልንጀራውን ይረዳዋል እንጂ በቁሙ ሊያርደው አይዳዳም።

ወያኔ የመሆን መብቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህንን ለመሆን የሄደበት መንገድ ግን በጣም ይደብራል። ድርጊቱ ሰሞኑን በፈረንሳይ ሃገር ከተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ ጋር ተመሳሳይ ነው የሆነብኝ። የክህደት ትንሽ የለውም። ልዩነቱ አባ መላ ያስጠጉትን ወገኖች በቁም አለመግደሉ ብቻ ነው።

አንዲት የዋህ ወይዘሮ፤ በፓሪስ ከተማ እመንገድ ላይ ወድቆ የሚለምን ኢትዮጵያዊ ወገን አግኝተው እጅግ አዘኑለት። እቤታቸውም ወስደው ማረፍያ ሰጡት። መሰረታዊ የሆነውን ነገር ሁሉ አሟሉለት። አምነው ያሳደሩት ይህ ሰው ግን ውለታቸውን በአሰቃቂ ሁኔታ መለሰላቸው። አራት ወር እንደቆየ ይህንን የሶስት ልጆች እናት ከትንሽ ልጃቸው ጋር በሴንጢ አርዶ ተሰወረ። አባመላ አብረውት ሲሰሩ የነበሩትን በቢላ ባያርዳቸውም በአነጋገሩ ስጋቸውን እንደበላው ነው የሚቆጠረው። አምነው አስተጉት ይህ ሰው እንደጴጥሮስ ጎህ ሳይቀድ ካዳቸው። የክህደት ቁልቁለት ይሏል እንዲህ ነው። «የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ!» ይላሉ አበው። ቃልን ማጉደል ምን ያህል ከባድ ነው!

ታማኝ በየነ እና አበበ ገላው ከብርሃኑ ዳምጤ ጋር በሳውዲው ቀውስ አብረው መስራት ሲጀምሩ በፍጹም ቅንነት እና በየዋህነት ነበር። ይህንን በማድረጋቸውም በርካታ ትችት ቀርቦባቸዋል። እነሆ አባ መላ ዛሬ ለቅልቅሉ እጅ መንሻ እነሱን በመሳደብ እንደመስዋዕት አቀረባቸው።

የብርሃኑ ዳምጤ አካሄድ ያሳሰባቸው ሁለት ወዳጆቼ በዚያን ሰሞን በዚሁ ጉዳይ ላይ በሰል ያለ አስተያየት ጽፈው ነበር። በልጅግ ዓሊ (ከፍራንክፈርት) እና እንግዳሸት ታደሰ (ከኦስሎ)። እነዚህን ጽሁፎች እንደገና እንድታነቧቸው እመክራለሁ። በልጅግ ዓሊ «ዘመንን ለማሰር» በሚለው ጽሁፉ ይህ ሰው እንደ ጴትሮስ ይክደናል ነበር ያለው።
…ለአንዲት የሰሙኑ የፖለቲካ ጥቅም ሲባል ብርሃኑ ደቡርን እላይ የሰቀላችሁት በኋላ እንደለመደው ሲክዳችሁ ስትንጫጩ መስማታችን አይቀርም። ትንቢት እንዳይመስላችሁ ደቡርን በደንብ አድርገን እናቀውቀዋለን። ቆዳችሁን ገፎ ይሸጠዋል፣ ደቡር ሃገሩን አይደለም እናቱንም ቢሆን ይደልላል። አታውቁት እንደሆን መርካቶ ላይ ሄዳችሁ የተሰራውን ግፍ ጠይቁ። እንኳን የቀይ ሽብሩን ፣ እነ ሽብሬን ረስተን የለም እንዴ !! ምን ይደንቃል።
ብሎ ነበር። እንግዳሸት ታደሰ ከኖርዌይ የጻፈውም ተመሳሳይ ነገር ነበር። «አባ መላ ልብ ሲበላ! » በሚለው መጣጥፉ «የዲያስፖራ ኃይል በአራዳ ስልትና በወያኔ ቆረጣ ለመሰንጠቅ ፣ የሚደረግም ጨዋታ ሊሆን ይችላል ብሎ መገመትም የዋህነት አይመስለኝም።» ነበር ያለው። እነዚህን መጣጥፎች ደግሜ ሳነባቸው ትንቢት ነው የመሰሉኝ። በወቅቱ ግን እነዚህን ጽሁፎች በድረገጽ በማውጣቴ የስድብ ናዳ ወርዶብኝ ነበር። አንዱ የፓልቶክ ታዳሚ እንዲህ ብሎ ነበር የጻፈልኝ። «የማናውቅህ እንዳይመስልህ! አንተ የዳዊት ከበደ ወንድም!»
የትኛው ዳዊት እንደሆነ ግን ግልጽ አላደረገልኝም። የአትላንታው ወይንስ የአውራምባው?

እርግጥ ነው። በፖለቲካ ቋሚ ወዳጅ ወይንም ቋሚ ጠላት የለም – ጥቅም እንጂ። በመርህ ላይ ሳይሆን ይልቁንም ለግል ጥቅም ሲሉ የሚዋዥቁ ሰዎች ናቸው ሀገርን የሚያጠፉት። በተለምዶ መሃል ሰፋሪዎች ይባላሉ። እንደዚህ አይነቶቹ ሰዎች በተቃዋሚውም ጎራ ነፍ ናቸው። ደጋፊ ሳይሆን ተደጋፊ ሆነው ለመኖር ሲሉ ብዙ ጥፋት ይሰራሉ። የሃይል ሚዛኑ እስካዘነበለ ድረስ ለአለቆቻቸው እጅግ ታማኝ ይሆናሉ። የሃይል ሚዛኑ ሲዛባ ደግሞ ለመካድ የመጀመርያዎቹ ናቸው።

ይህ የመርካቶ ቁጭበሉ ሼም አያውቅም። ትንሽ ብትጠብቁት እንደገና ይመለሳል። በዚህ አይነት ሰው ላይ እምነት መጣል እና መስጋት ከየዋህነት ያለፈ ነው። አንድ ጅል ትምህርት ቤት ሲሄድ የሙዝ ልጣጭ አዳልጦት ወደቀ። ከትምህርት ቤት ሲመለስ ያችኑ የሙዝ ልጣጭ አይቶ ቆመ። ከዚያም ማልቀስ ጀመረ። ለምን እንደሚያለቅስ ሲጠየቅ ወደ ልጣጩ እያመለከተ እንዲህ አለ። «እንደገና ልወድቅ ነው።»


አባ መላ እና መላ ያጣው ንግግራቸው (በዳጉ ኢትዮጵያ)

$
0
0

አቶ ብርሃኑ ዳምጤ (አባ መላ) በቅርቡ ስላደረጉት የአቋም ለውጥ ለቢንያም ከበደ (ቤን) የሰጡትን ቃለ መጠይቅ አነበብኩት፡፡ ላልተጠበቀው የ180 ዲግሪ የአቋም ለውጥ በመንስኤነት ከጥቅመኛ ፖለቲከኝነት እስከ የጠበቁትን አለማግኘት በርካታ ምክንያቶች እየተጠቀሱ በብዙዎች ትንታኔ እየተሰጠበት ይገኛል፡፡ እኔ በዚህ ረገድ ምንም ለማለት አልፈልግም፡፡ ይልቁንስ በቃለ ምልልሳቸው ኢሳትን በተመለከተ በሰነዘሯቸው አንዳንድ የተሳሳቱ ነጥቦች ላይ ጥቂት ብል እመርጣለሁ፡፡ የትኩረት ነጥቦቼን በተናጠል ተራ በተራ እዘረዝራለሁ፡፡

Aba Mela
“ምንም አይነት የዜና ምንጭ የሌላቸው”
አቶ ብርሃኑ ስለኢሳት ከተናገሯቸው ነጥቦች የመጀመሪያው “ኢሳት ምንም አይነት የዜና ምንጭ የለውም” የሚል ነው፡፡ እውነት ለመናገር ራሳቸው አቶ ብርሃኑም በዚህ ንግግራቸው የሚያምኑበት ከሆነ አስቂኝ ነው፡፡ እንዴ አቶ ብርሐኑ፡- መቼም የጠቅላይ ሚኒስትርዎትን ሞት ቀድመው የሰሙት ከኢቲቪ አልያም ከፋና አይደለም፡፡ የብአዴን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለምነውን አስፀያፊ ንግግር ከዝግ የካድሬዎች ስብሰባ ላይ ቀድቶ አየር ላይ ያዋለው የሰሞኑን ወዳጅዎ (መቼም እርስዎ በዚህ ተለዋዋጭ አቋምዎ ዘላቂ ወዳጅ አይኖርዎትም ብዬ ነው) አቶ ቢንያም አይመስለኝም፡፡ ኸረ ስንቱ ስንቱ… ከጉራ ፋርዳ የአማራ ተወላጆች መፈናቀል እስከ የኦህዴድ ውስጣዊ ህንፍሽፍሽ… ኢሳት ይህን ሁሉ ከህዝብ ተደብቆ የነበረ መረጃ አደባባይ ያወጣው ያለአንዳች የመረጃ ምንጭ ነው ካሉን በአመክኒዮ ሳይሆን በስሜት እንደሚነዱ በራስዎ ላይ እየመሰከሩ ነው፡፡
“የዜና ምንጫቸው በአብዛኛው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ነው”
ይህ ነጥብ ደግሞ አስቂኝነቱ ያመዝናል፡፡ ኢሳት የኢቲቪን ዜና “ትዊስት እያደረገ የመጀመሪያውን መጨረሻ የመጨረሻውን መጀመሪያ” አድርጎ የሚያቀርብ ከሆነ አራተኛው የኢቲቪ ቻናል ሆነ ማለት ነው፡፡ የኢቲቪን ዜና ዳግም የሚያሰራጭ (Rebroadcast) ጣቢያ ከሆነ ደግሞ እኔን ጨምሮ በሚሊዮን የምንቆጠር ኢትዮጵያውያን አማራጭ የመረጃ ምንጭ ባላደረግነው ነበር፡፡ ለምን ቢሉ ኢቲቪን ዲሽ መትከል ሳያስፈልገን፤ አንዱ የስርጭት ሞገድ ሲዘጋ በመቶዎችና በሺዎች የሚቆጠር ብር ከእለት ጉርሳችን ነጥቀን ለዲሽ አስተካካዮች ሳንከፍል መከታተል እንችላለን፡፡ እውነቱን ለመናገር የኢሳት የተሰሚነት ሚስጥር እርስዎ ከተናገሩት ተቃራኒው ነው፡፡ ከአሰልቺውና ከእውነት ከተጣላው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ፕሮፖጋንዳ የሚያስጥል አማራጭ አድርጎ ኢሳት ራሱን ማቅረቡ ነው የተሰሚነቱ ምክንያት፡፡ እስኪ ለዛሬ ለእውነት ታማኝ ለመሆን ይሞክሩና የኢቲቪንና የኢሳትን የዜና ፕሮግራሞች ይከታተሉ፡፡ ኢቲቪ የሐረር የውኃ ችግር እንደተቃለለ “አንዳንድ ነዋሪዎችን” እማኝ አድርጎ ሲዘግብልዎት ኢሳት ግን በህዝቡ አዕምሮ ውስጥ የሚብሰለሰለውን የሐረር የግንብ መደዳ ሱቆች ቃጠሎ ክስተት ተጎጂዎቹን እያነጋገረ ያስደምጥዎታል፡፡ እርስዎ በሐረር ከተማ ቢኖሩ አሊያም በከተማው ውስጥ የሚኖር አንዳች የቅርብ ዘመድ ካለዎት የኢቲቪን “ሐረር ሠላም ነው ምንም አልተፈጠረም” የዘወርዋራ ፕሮፖጋንዳ ለመስማት የሚያስችልዎት አንዳች ፍላጎት ይኖርዎ ይሆን?
“ተአማኝነት የሌለው”
በቅርቡ የብአዴን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የአቶ አለምነውን ስድብ-አዘል ንግግርና የፓርቲያቸውን የዝምታ ስምምነት በመቃወም በባህር ዳር ከተማ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተሳተፉበት ደማቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሒዶ ነበር፡፡ ሠልፈኞቹ ለተቃውሞ የወጡበትን የአቶ አለምነውን ንግግር የሰሙት በሌላ በማንም ሚዲያ ሳይሆን በኢሳት ነው፡፡ ከአዲስ አበባ በ500 ኪ.ሜ ርቀት የሚኖሩ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በኢሳት የሰሙትን መረጃ አምነው ለተቃውሞ የባህር ዳር ከተማን ጎዳናዎች አጥለቅልቀዋል፡፡ ተአማኝነት ማለት እንግዲህ ከዚህ በላይ ምን ማለት ይሆን?
“ኢሳት ከግንቦት ሰባት ውጪ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶችን አያስተናግድም”
አቶ ብርሐኑና እኔ የምንሰማው ሁለት የተለያዩ ኢሳቶችን ካልሆነ በቀር በየእለቱ የኢሳት ፕሮግራሞች የአንድነት፣ የሠማያዊ፣ የአረና ወዘተ እንቅስቃሴዎችና መግለጫዎች ሰፊ ሽፋን የሚያገኙት በኢሳት ነው፡፡ ቀደም ሲል የጠቀስኩት የባህር ዳር የአንድነት ፓርቲና የመኢአድ የተቃውሞ ሠልፍ የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኘው በኢሳት ነበር፡፡ ኢቲቪማ በሠልፉ ተደናግጦ ስለሰልፉ አንዳች ቃል ሳይተነፍስ ይልቁንስ “መድረክ አንድነትን ከአባልነት ማገዱን” እያጋነነ ሲዘግብልን ነበር፡፡ “ተቃዋሚዎች ተከፋፈሉ” ነው መልዕክቱ፡፡ ሁለት ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች (አንድነት ፓርቲና መኢአድ) በትብብር መሬት-አርዕድ የተቃውሞ ሠልፍ ማድረጋቸው ሳይሆን አንድ ፓርቲ ለጊዜው ከመድረክ መታገዱ ለገዢው ፓርቲ የሚጠቅም ዜና ስለሆነ ሽፋን ያገኛል- በኢቲቪ መስፈርት፡፡
“በኢሳት ከግንቦት ሰባት ውጪ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ሽፋን አያገኙም” ለሚለው የአቶ ብርሐኑ አስተያየት ራሱ ገዢው ፓርቲ ከሳምንታት በፊት በሐገር ውስጥ በህጋዊነት ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች መሪዎች በኢሳት መግለጨ መስጠታቸው ህገወጥ ነው ሲል መክሰሱና አንድነትና ሠማያዊ ፓርቲም “ይህን ማድረግ መብታችን ነው” ሲሉ በጽኑ መቃወማቸው ጉልህ ማስተባበያ ነው፡፡ ሌላው ቢቀር ግንቦት ሰባት “ከኤርትራ በማገኘው ድጋፍም ጭምር ተጠቅሜ የአገዛዝ ስርዓቱን አወርዳለሁ” ሲል በሰጠው መግለጫ ላይ ጊዚያዊ የሽግግር ምክር ቤቱ ተቃውሞ ማሰማቱን ከዋና ፀሐፊው አንደበት የሰማነው በዚሁ በኢሳት እንደነበት አቶ ብርሐኑ አይዘነጉትም ብዬ አምናለሁ፡፡
በአጠቃላይ የያዙትን የፖለቲካ አቋም በማናቸውም ምክንያት ትቶ የአቋም ለውጥ ማድረግ ሊከበርለት የሚገባ የማንም ሰው መብት ነው፡፡ ነገር ግን አዲስ የተቀላቀሉት ካምፕን ደስ ለማሰኝትና ድርጎ ቢጤም ለማግኘት በማሰብ የባሰ ትዝብት ላይ የሚጥል ንግግር መናገሩ ፋይዳው ብዙም አይታየኝም፡፡ አገዛዙ እንደሆነ ደጋፊህ ነኝ ብሎ ለሚመጣለት (በተለይም ከተቃዋሚው ጎራ) ከህዝብ አንጡራ ሐብት ላይ ዘግኖ ላለመስጠት የሚያስችል አንጀት እንደሌለው የታወቀ ነውና አቶ ብርሐኑም ያሰቡትን ለማግኘት ብዙ መቀባጠር የሚኖርብዎት አይመስለኝም፡፡ አበቃሁ!

ትዝብት –ደርሶ መልስ ዲያስፖራ (ኢትዮጵያ ደርሶ የመጣ ዲያስፖራ የሚነግራችሁ እውነት) (አንደኛ)

$
0
0

አትክልት አሰፋ (ቫንኩቨር) – ጋዜጠኛ

ነገሩ የሆነው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ነው። ቆነጃጅት ወጣት ሴት ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውጭ ባሉ የከተማው ደለላዎች ጋር በመተባበር እጅግ ዘግናኝ ስራ ይሰራሉ። ደላሎቹ የቆነጃጅቶቹን ተማሪዎች ፎቶ የያዘ ትልቅ ካታሎግ ይዘው ከአዲስ አበባም ሆነ ከአቅራቢያው ከተሞች አለዚያም ከዚያው ከዲላ ከተማ ብቅ የሚሉ ሃብታም ደንበኞቻቸውን የተማሪ ኮረዶችን ፎቶ በመስጠት ያስመርጣሉ።

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

ሰውየው ውብ ወጣት ተማሪ ኮረዳ እንደሚፈልግ በሰው በሰው የተገናኘውን ደላላ ይጠይቃል። እናም ከተሰጠው የፎቶ ድርድር ላይ ማመን ያቃተውን የአንዷን ውብ ፎቶ እያሳየ ‘ይህችን ታውቃታለህ?’ ሲል ይጠይቃል። የደላላ መልስ አንድ ነው… ሁሉንም ስለሚያውቃቸው አልተቸገረም ‘አዎ እሷን ይፈልጋሉ?’ ሲል ይጠይቃል። ሰውየውም ‘እባክህ’ ሲል በመማጸን ፈቃደኝነቱን ይገልጻል። ከፊቱ የመጣለትን ገቢ ተደራድሮ ልጅትን ለመጥራት ይሮጣል። ደላላው።

እናም ቆንጅት ተበጃጅታ፣ አምራና ደምቃ ትመጣለች። በቀጥታ ወደ ሰውየው መኪና ስትደርስ ሰውነቷ ይርዳል። በቁጣ አይኑ የተንቀለቀለው ሰውየም ወደ ልጅቷ ያፈጣል… በቀጥታ ተንደርድሮ የልጅቷን ክርን ይይዛል… ደላላው እየሆነ ያለውን ሊረዳ አልቻለም… የልጅቷን እጅ የያዘው ሰው (ደንበኛ) የልጅቷ ወላጅ አባት ኖሯል።

ኢትዮጵያ ደርሶ የሚመጣ የውጭ ሀገር ነዋሪ (ደርሶ መልስ ዲያስፖራ) በተለያየ አይነት እይታ የተለያዩ እውነታዎችን ይዞላችሁ ይመጣል።

አንዳንዱ የህንጻውን ግንባታ አዳንቆ ሲያወራ፤ ሌላው ስለጭፈራ ቤቶች ይዘክራል። ጓደኞቹን በስራ ብዛት ሊያገኝ እንዳልቻለ የሚያወራላችሁ እንደመኖሩ ሁሉ በስራ አጥነት ችግር የተነሳ ዱርየ መበራከቱን የሚተርክላችሁ አታጡም። የቆነጃጅቶችን ውበትና የዳንኪራ ቤቶችን ሁናቴ የሚነግራችሁ፤ በየቡና ቤቱ ብሎም በየትምህርት ቤቱ ያሉ ወጣቶችን ችግር ያስረዳችኋል። የሀገሪቱን እድገት በኮንስትራክሽን መጥለቅለቅ የሚያጫውታችሁ፤ በመንገዱን መቆፋፈር ሰው ስለመማረሩ በማንሳት ያትትላችኋል። አዲስ አበባን በመመስረት ላይ እንዳለች ታላቅ ከተማ አድርጎ የሚተርክም አታጡም።

ይሄ ሁሉ እንደ እድገት በአንዲት መንግስት የሚባል አካል አላት በተባለች ሀገር መታየቱ ምኑ ይገርማል?። አንዳንዴ ሀገሩን አይቶ ዘመድ ወዳጅ ጠይቆ መምጣትም ሆነ ሰው ሀገሩ ደርሶ መመለሱ እጅግ መልካም ነገር ነው። ያየውን ግልብ ነገር ከራሱ አይን ጥግ ስር አንጻር ብቻ ተመልክቶ በሰዎች ላይ የሚደርስን ስቆቃ ሸፋፍኖ ያለጥናት የተሰሩ መንገዶችንና ህንጻዎችን እንደትልቅ ለውጥ ማውራት ግን የሞራል ጥያቄን ያመጣል።

በእርግጥ የውብ ሀገር ነችና ውቦች ሊኖሩ ይችላሉ። መሸታ ቤቶቹም ደማምቀው ሊሆን ይችላል። ህንጻ ግምባታውም ቢጧጧፍ አያስነውርም። መንገዶች ተንጣለው ቢታዮም ጸጸት የሚገባው የለም። ነገር ግን ሰው በቀላሉ ቆሎ ሽጦ ይኖርበት ከነበረ መንደር ተባሮ መግቢያ ያጣበት ሀገር፤ ውሃ ልማት የቆፈረውንና ውሃ ቧንቧ ቀብሮ ያበጀውን መንገድ ነገ ቴሌ የሚያፈርሰው ከሆነ… ከዚያም ማዘጋጃ ቦይ ተደፈነ ብሎ ከተረተረው… ወጣት እንስት ህጻን ታናሽ እህቷንና ወንድሟን ትምህርት ቤት ለመስደድ መንገድ ከወጣች፤ ጥቂት የባለጊዜ ልጆች የሚሰሩት አጥተው በተንፈላሰሱባት ሀገር መለመንን ተጠይፈው ዱሮ የነበራቸውን ጽዱ ልብስ ለብሰው ፊታቸውን የከለሉ ሰዎች በየጥጋጥጉ የሚለምኑባት ሀገር ከሆነች… አባት ትምህርት ቤት ብሎ የላካት ወጣት በኮሌጅ ያለውን ፍላጎቷን ለማሳካት ገበያ መውጣት… ዘግናኝ ነው…

የሚሰራው መንገድ ተሸርሽሮ ከአመት በላይ አገልግሎቱ አልቆለት ተቦርቡሮና ውሃ ቋጥሮ የሚታይበት ሀገር እየገነቡ መሰረት መጣል አይቻልም ነው ጥያቄው። ደረጃቸውን ባልጠበቁና በይድረስ ይድረስ የተሰሩ ህንጻዎች ጋጋታ የከተማንም የሀገርንም እድገት ሊያሳዩ አይችሉም ነው እየተጮኸበት ያለው ነገር። ፍትህ ራሷን ችላ የምትራመድበትን ሀገር የሚመራ መንግስት ይኑር ነው ልፈፋው። የህወሃት ሰዎችና ጥቂት አሸርጋጆች የሚያደርጉት አገራዊ ጥፋት ይቁም። ልጆቻችን እርስበርስ የዚህና የዚያ ብሄር ወይንም ከወዲያ አለዚያም ከወዲህ መንደር የመጡ እየተባባሉ በጥርጣሬ እየተያዩ የሚኖሩበትንና የሚያድጉበትን ሀገር እናፈራርስ ነው እሪታው። የህወሀት አለያም ጥቂት ሽርጉደኞች በገፍ የሚገነቧቸው ህንጻዎች ከሙስና ባሻገር ሆኖ ራሳቸው ኢንጂኒዬርና አርክቴክት ሆነው የሚገነቡት ሀገር ሀገር አይሆንም ነው ጉዳዩ።

22 አካባቢ የተሰራው ጎላጎል ህንጻ ባለጊዜው ባለቤት ህንጻውን ሲያስገነባ ዋናው መንገድ ውስጥ መግባቱን ያየ መሀንዲስ ወይንም ኢንጂኒዬር ‘አግባብ አይደለም፤ ወደፊት መንገድ ይዘጋል’ ብሎ ምክር ቢሰጠው ‘እኔ ያልኩህን አድርግ’ ብሎ ጀርባውን የተማመነው ባለቤት ሲያዘውና ያ ባለሙያ የታዘዘውን በማድረጉ ግንባታው ከተጠናቀቀ በኋለ አሁን መንገዱን የዘጋውን ህንጻ የሚደፍረው ጠፍቶ፤ መረማመጃው ዘግቶ መታየቱ የሚወራው ዝም ብሎ ከመሬት ተነስቶ አይደለም።

አሁንማ የህወሃት ሰዎች እጅግ ከመድፈራቸው የተነሳ አዲስ አበባ ውስጥ በስማቸው ሆኗል ፎቅ የሚያስገነቡት ተክላይ ህንጻ፣ ገብረጻዲቅ ህንጻ… ብሎ ያጫወተኝ ወዳጄ ታዲያ ምን ችግር አለው? ስለው ‘ምንም ችግር የለውም በህዝቡ ውስጥ ግን የማህበራዊ ህይወት መራራቅንና ሃሜትል ያስከትላል ብሎም ህዝቡን እነሱ እና እኛ የሚያስብል የሳይኮሎጅ ጣጣ ውስጥ ከቶታል።” አለኝ

ሀገሪቱን የህወሃት ጄኔራሎችና መኮንኖች ብቻ በሀብት የወረሯት ሀገር ተሸክሞ የት እንደሚደረስ ማሰብ ሰው መሆን ነው። ይህ ወዳጄ ታዲያ በአንጻሩ የሽንኩርትን ገበያ ለማየት ጉሊት ወርዶ ያየውን ጉድ በልኩ አስተውሎ መጥቷል። አንድና ሁለት ራስ ትንንሽ ሽንኩርት አልያም ቲማቲም ለሳምንት ለማብቃቃት የሚሰቃይ ህዝብን ይዞ ጉዞው የት ነው የሚያደርሰን።

የአገሪቱን የዘር ችግር ጥግ ላይ መድረስ ባለፈው 767 አውሮፕላንን ይዞ ጄኔቫ የገባው ወጣት ረዳት አብራሪን በሚመለከት መግለጫ የሰጡት ሬድዋን ሁሴን “ጠላፊው ከየት ነው?’ ተብለው ሲጠየቁ ‘ኢትዮጵያዊ ነው’ ብለው ሲመልሱ አረ ከየትኛው ክልል ተብለው መጠየቃቸው ጉድጓድ ውስጥ የሚከት ቅሌት ነው። መልሳቸውም እረሪሪሪሪሪ የሚያስብል ነበር። ‘ከየትኛው ብሔር እንደሆነ አልታወቀም።’

መጠጥና ዳንኪራ ቤቶች

ከ5 ሚሊየን ህዝብ በላይ (እስከ 8 ሚሊዮን ይገመታል) የሚኖርባት አዲስ አበባ የጭፈራ ቤቶችን ብዛትና የጨፋሪውን አይነት የነገረኝ ወዳጄን ቀኑን ሙሉ ሲተራመስ የሚውለው አዲሳቤ በጊዜ በ12 ሰዓት ከቶ በየፊናው ሲገባ ከተማው ምን ያህል ጭር እንደሚል አላስተዋለም። 100 የማይበልጡ ምሽት ቤቶች (አጋንኘው ነው) 100 ሰው እያንዳንዳቸው ቢያገኙና ቢያስጨፍሩ 10ሺህ ሰው… እንጨምረው እና 50ሺህ ሰው በምሽት ስለጨፈረና ስለደነከረ ሀገር በጥጋብ እንደዘለለ ማውራት ነውር ነው ነው ጨዋታው። ይሄንኑ ግምት እናስላው ከተባለ የገዥው ህወሃት/ኢህአዴግ ባለስልጣናትና ጥቅም ተሻራኪዎች 70 በመቶውን ቢያነሱ 15 በመቶ በዲያስፖራና ዘመዶች እንዲሁም የተቀረው ለፍቶ አዳሪ አለያም ከቤተሰቡ የሚቃርም ሊሆን ይችላል።

ለነገሩማ የዘመነኞቹ ሰዎች ልጆች የሚገቡበት ቡና ቤት ውስጥ ቀድሞ የገባ ሌላ ደንበኛ ሾልኮ እንዲወጣ የሚደረግባት ምድር። በድርድር የታሰረ ብር ለአስተናጋጅ ተሰጥቶ ቆጥረሽ ውሰጅ የሚል ረብጣው ያጨናነቀው የዘመኑን ሰው ማየት የተለመደ መሆኑንም እየሰማን ነው።

ምን እዚህ እኛ በብርድ እየወጣን ሰላማዊ ሰልፍ እያልን እንጮሃለን እነሱ ሚሊየነሮች ሆነዋል ያለኝና ሀገር ቤት ሄዶ በጓደኛው የቀና ሰው ያጫወተኝም አለ። ያ ጓደኛው ከዘመንኛ ሰዎች ጋር ገጥሞ ህዝብ እየቦጠቦጠ መሆኑን የነገረኝ ደርሶ መልስ ዲያስፖራ… አሁንም እዚህ ኖርዝ አሜሪካ ከተመለሰ በኋላ እዚያው አገር ቤት ቢሆን እንደጓደኛው ሚሊየነር ይሆን እንደነበር ሲያወጋኝ በመቆጨት ነበር። ዘመንኞቹና ጓደኛው የሚቦጠቡጠው ህዝብ ስቃይ በሚሊየን ብር ተጋርዶበት። አረ እየተስተዋለ! እዚያኮ ሀገር እየተቆራረሰ ነው! አረ ስለአምላክ! ሀገሪቱም በመንደር እየተተበተበችኮ ነው! ስለእመብርሃን! ምድራችን ፍትህ የጠፋባት ሆናለችኮ! በሽብርተኛ ስም ስንቱ ታጎረ… አረ ስለአላህ! ሰው ኑሮ መረረኝ እያለ ነው እኮ! እንኳን ከአሜሪካ ከመንግስተ ሰማያትም አመጣኻለሁ የሚል ለስራው ብቁ ያልሆነ ሰው የሚሾምበት ሀገር ውስጥ የሚኖር ህዝብ እኮ ነው የያዝነው። ጭራሽ የሶማሌ ክልል ባለስልጣን ይባስ ብሎ ምኒባስ ታክሲ በከተማ እንዳይገባ ብሎ በራሱ ስልጣን አግዶ እገዳውን የጃፓን መንግስት ቢመጣም እንኳን አልቀበልም እያለ እኮ ነው ጎበዝ… ሰሚ የለም እንዴ በግዜር!?

ለዛሬ ላብቃ!

ቸር ለእናንተ!!!

ሙሰኞችና “ሙሰኛው” ፀረ ሙስና

$
0
0
(ናትናኤል ካፕትይመር)

(ናትናኤል ካፕትይመር)

ናትናኤል ካብትይመር (ኦስሎ ኖርዌይ)

. . . . . . .የኢትዮጲያ ፀረ ሙስና ኮሚሽን የህዝብንና የመንግስትን ንብረት ለግል ጥቅማቸው በማዋል ክስ የመሰረተባቸውን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን  . . . . . . የኢቲቪ ዜና

. . . . . ጉድ ፈላ በቃ ቀጥሎ ሴትዮዋ ነች  . . . . . የዋህ ኢትዮጲያውያን

. . . . . . . እባካችሁ በጥቂት ሺህ ብሮች የወር ደሞዝ የህዝብ አገልጋይ ነን እያላችሁ የሰባት ሚሊዮን ብር መኪና አትንዱ . . . . .” አፈጉባኤው

. . . . . . .የቀድሞው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሙስናን በማጋለጥ ጋር በተያያዘ በታሸገ ውሃ ተመርዘው ነው የሞቱት መባሉን ባናረጋግጥም ከቅርብ ግዜ ወዲህ ግን በኦሮሚያ ክልል መንግስታዊ ስብሰባዎች የታሸገ ውሃ መቅረብ መቆሙን አውቀናል  . . . . . . ለስርዓቱ እጅግ የቀረቡ የመንግስት ጋዜጠኞች
alemayehu atomsa
ባለፈው ሰሞን ጥቂት የመንግስት ባለስልጣናት በሙስና ሰበብ ተብሎ ዘብጥያ ሲወርዱ የታሳሪዎች ቁጥር ከወትሮው ለየት በማለቱ ፀረ ሙስና ስራውን ጀመረ ብለው ተስፋ የጣሉ ኢትዮጲያውያን ጥቂት አልነበሩም። እንደው የህዝባችን የዋህነት ነው እንጂ ፀረ ሙስና ከተመሰረተ ጀምሮ አንድም ቀን እንደስሙ ስራውን ሰርቶ እንደማያውቅ ፣ ጥቅሙም ሌላ እንደሆን የታወቀ ነው። እንጂማ ገና ያኔ እነ አቶ ታምራት ላይኔ ፣ እነ አቶ አባተ ኪሾ የመሳሰሉት በሙስና ሰበብ ወደ እስር ሲወርዱ በህዝብ ገንዘብ ጠግበው የደለቡ የመንግስት ባለስልጣናትና አጋፋሪዎቻቸው የውስኪ ብርጭቆአችውን እያጋጩ ሲሳለቁ ማንም የነካቸው አልነበረም። ምክንያቱም ነገሩ ሌላ ነው። የፀረ ሙስና ኮሚሽንም ለመንግስት የሚሰጠው ጥቅም ሌላ ነው።

ሁሌ ሳስበው የሚያስገርመኝ እንደ ህወሃት መንግስት የተለያዩ አለማቀፋዊ መሰረት ያላቸውን ህግጋትና ደንቦች ለራሱ የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ እየሸነሸነ የሚያውል መንግስት ያለ አይመስለኝም።

የኢትዮጲያ ፀረ ሙስና ኮሚሽንን የህወሃት መንግስት ሲያያቸው ያላማሩትን ፣ የውስጥ ጉዱን የሚያወጡበት የመሰለውን የገዛ ባለስልጣናትና ሹመኞቹን ማስወገጃ አርጎ ይጠቀመዋል ፥

የፀረ ሽብር ህግን ህዝብ የወደዳቸውን ፣ አካሄዳቸው ያሰጋውን ፣ እውነትን ለህዝብ የሚያጋልጡትን ጋዜጠኞችንና አማራጭ የፖለቲካ ሃሳብ አመንጪ አካላትን ማስወገጃ አርጎ ይጠቀመዋል ፥

መሰረታዊ የስራ ሂደት ለውጥን (Business Process Reengineering) የህወሃት ካድሬዎችንና በሲቪል ሰርቪስ በኢሃዴጋዊ አገዛዝ ያጠመቃቸውን ጆሮ ጠቢዎች በየመንግስት መስሪያ ቤቶች ለመሰግሰግ ይጠቀመዋል ፥

አገር አቀፍ የመረጃ ደህንነት ጥበቃ (National Information Network Security) ሲስተሙን የተለያዩ የዜና አውታሮችንና ድረ ገፆችን በሃገር ውስጥ እንዳይታዩ ለመዝጋትና አማራጭ የፖለቲካ ሃሳብ አመንጪ አካላትን መረጃ ለመበርበሪያ ይጠቀመዋል ፥

አንዳቸውም ለተፈጠሩበት ፍልስፍና በሃገራችን በአግባቡ ስራ ላይ ሲውሉ አይታዩም : ሌሎችም ብዙ አሉ።

“ኧረ ይሄ አሰራር መጥፎ ነው” ሲባል ዋናውን ጥያቄ ሆን ብሎ በማድበስበስ “ህጉን የገለበጥነው በቀጥታ ካደጉት ሃገራት ነው” ይባልና ያልተጠየቀው ይመለሳል።

“የለም የለም ህጉን አተረጓጎማችሁ ልክ አይደለም” የሚል ጫን ያለ ጠያቂ ሲመጣባቸው “መጠነኛ የአፈፃፀም ችግር ስላለ ነው በቅርቡ እንቀርፋለን” ይላሉ ከዛሬ ስንት አመት ጀምሮ።

ወደ ዋናው ሃሳቤ የሙስና ጉዳይ ልመለስና በአንድ ወቅት ከአንድ ጋናዊ ጓደኛዬ ጋር ስለ አህጉራችን አፍሪካ መሪዎችና ባለስልጣናት መረን የወጣ ሙስናና ገንዘብ መውደድ ባህሪ ስንወያይ በማልረሳው መልኩ እንዲህ አለኝ

“የሚገርምህ በምሳሌ ባስረዳህ የአፍሪካ ሃገራት ፕሬዝዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትር በሃገራቸው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ሲወያዩ ‘. . የሚያስፈልገን ከሃምሳ ሚሊዮን ዶላር በላይ ነው ስለዚህ እነዚህን ሃገራት ብድርና እርዳታ እንጠይቃለን በተጨማሪም ከህዝቡ መዋጮ እንጠይቃለን . .’ ብለው ስብሰባውን ይቋጫሉ ነገር ግን ሁለቱም እያንዳንዳቸው ከመቶ ሚሊዮን ዶላር በላይ በአውሮፓና አሜሪካ በሚገኙ ባንኮች በድብቅ እንዳስቀመጡ ይተዋወቃሉ።  መሪዎቻችን ከግለኝነትና ከስግብግብነት ካልወጡና ከነዚህም ችግሮች የፀዳ አመራር ካላገኘን ገና የአፍሪካችን መከራ ብዙ ነው” አለኝ።

እኔም የሃገሬ መንግስት ከቀበሌ ጀምሮ የሾማቸው ሹመኞችና ባለስልጣናት ፣ የሚነዷቸው መኪኖች ፣ የሚኖሩበት ውብ ቪላዎች ፣ ታማኝ ምስኪን የመንግስት ሰራተኞች ፣ እንደ ቁመናው ያላማረበት የፀረ ሙስና ኮሚሽን ህንፃ ፣ የኢቲቪ ሙስና ነክ ዜና በቅፅበት በአምሮዬ ውልብ ውልብ እያሉ አለፉ።

በኢትዮጲያ የመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ አነስተኛ መሆኑን ሁላችንም እናውቃለን። በተያያዘም የመንግስት ባለስልጣናትና ሹመኞችም የመንግስት ሰራተኞች መሆናቸውንም እናውቃለን። ይህ ማለት ደግሞ የመንግስት ባለስልጣናትና ሹመኞች ደሞዛቸው ከመንግስት ሰራተኞች እኩል በመንግስት የደሞዝ እርከን መሰረት ነው ማለት ነው። ሌላው የመንግስት ሰራተኛ በኑሮ ውድነት ናላው ሲዞር ባለስልጣናቱ ግን ደሞዛቸው ስንት እንደሆነ እንኳን አያውቁትም ምክንያቱም የገንዘቡ መጠን የሚነዱትን የሚሊዮኖች ብር መኪና የቀናት ነዳጅ እንኳን አይሸፍንም ፥ ታዲያ ማወቁ ምን ያረግላቸዋል።

ደሞዛቸው ትዝ የሚላቸውና ብዙ ግዜ በርካቶቻችንን የሚያስገርመንና በቁጭት ፈገግ የሚያስብለን የገቢ ማሰባሰቢያ ወይም ቴሌቶን ሲዘጋጅ “ክቡር ሚኒስትር እከሌ የአንድ ወር ደሞዛቸውን ሰጥተዋል ሞቅ ያለ ጭብጨባ” ሲባል ወይም የሚንስትሮቹ ሚስቶች ምን ያህል ቆጥበው ፣ ለፓርቲያቸው አዋጥተው ፣ ተቸግረው ፣  ተቸጋግረው ፣ ልጆቻቸውን እንደሚያስተምሩ ሲያወሩ ነው።

ኧረ ይሄ ነገር ልክ አይደለም ሲባል ፥ “ሃገር ለማሸበር” ወይም “የጥላቻ ፖለቲካ” ይባላል። ሲጀመር ውል ያለው የፖለቲካ ስርዓት የህወሃት መንግስት የለውም ሲቀጥል . . . . . . . .ግድ የለው አሁን ከዋናው ርዕሴ አልውጣ።

በርካታ የመንግስት ሹመኞችና ባለስልጣናት ቢሮ እንደው እግር ጥሏችሁ ከሄዳችሁና ቀና ብላችሁ አስተውላችሁ ከሆነ በግርግዳቸው ላይ የለጠፏት ወረቀት “ታማኝነት ፣ ግልፅነት ፣ የህዝብ አገልጋይነት ፣ ቅንነት ፣ የመሳሰሉት ውብ ቃላቶች” በተርታ ተለጥፈው ይታያሉ ነገር ግን ዝቅ ብላችሁ የሹመኛውን ወይም የባለስልጣኑን ፊት ስትመለከቱት “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል” የሚባለው አበው ለምግብ ይሁን ለህዝብ ገንዘብ በውል ሳይለዩ ያወረሱን ብሂል ሁለመናውን ወርሶት ታዩታላችሁ። ሹመኛና ባለስልጣን እየተፈራረቀ “ምነው በኔ ተጀመረ እንዴ” እየተባባለ ያችን ምስኪን ሃገር ይግጣል።

ሙስናና ንቅዘት በሃገር ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊም ሆነ ዲሞክራሲያዊ እድገት ላይ ያለው አሉታዊ ተፅእኖ እጅግ ብዙ ነው። ስልጣንን መከታ በማድረግ የሚገኝ ገቢ መዘዝ የሃገርን ሃብት በማውደም ብቻ አያበቃም። የመንግስት ስልጣንና ሹመት ሃገርንና ህዝብን ማገልገል መሆኑ ይቀርና የቤተሰብ እንዲሁም የዘመድ አዝማድ የገቢ ምንጭና ህልውና ወደመሆን ይሸጋገራል። በዚህም ሳቢያ ደግሞ በተገቢው መልኩ የአገልግሎት ግዜ ሲያበቃ በሂደት የመተካካት ፣ ለተተኪው ስልጣንን ማሳለፍ ወይም መልቀቅ የሚለው መሰረታዊ የዲሞክራሲና የሃገር እድገት መርህ ይጣስና ስልጣንና ሹመት የቤተሰብና የዘመድ አዝማድ የኑሮ ምሰሶ ሆኖ ስለሃገር እድገት ማሰብ በራስ ወዳድነትና በግለኛ የማይጠረቃ ፍላጎት ይተካና ስልጣን ወይም ሹመት ላይ እስከወዲያኛው ሙጭጭ ማለትን ያመጣል።

በቅርቡ የተካሄደው የኢህአዴግ ስብሰባ  “ . .  የፓርቲያችን ዋናው ችግር ሙስናና አድር ባይነት ነው ስለዚህ . . . “

የሚቀጥለው የኢህአዴግ ስብሰባ “ . . . . ባለፈው ያልናችሁ ዋናዎቹ ችግሮቻችን ሙስናና አድርባይነትን የምንዋጋበትን እቅድ በአፋጣኝ በሚቀጥሉት አምስት አመታት ውስጥ እናወጣለን  . . . . .”

እኔ በዚህች ላብቃ  . . . . . መስናና ዘረፋው ግን አምሮበት እንደቀጠለ ነው።

natnaelkab@gmail.com

 

በለው! ቄንጠኛ ዳንስ በዕንባ ሲደንስ

$
0
0

haile Mariam Desalegn 1

ሥርጉተ ሥላሴ 13.03.201 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

siraateምን አለባቸው አልሞተባቸው፤ ጥቁር አለበሱ፤ የተራበ ወግን የላቸው፤ የታሰረ ሥጋ የላቸው፤ ባለጊዜ እንዲህ በቄንጥ ዳንሱን ያስነኩት፤ ይጨፍሩ! በጣም አምሮባቸዋል! ተዋጥቶላቸዋልም። ሂዶላቸዋልም። ሚሊዮኖች ጉርሻ ፍላጋ ለትራፊ በረድፍ ተሰልፈው ከጠኔ ጋር ተፋጠዋል። ሚሊዮኖች ከቦታ ቦታ ተራ ዜጋ ናችሁ ተብለው ይፈናቀላሉ። ሺዎች „ኢትዮጵያዊ“ እተባሉ በዬአረብ ሀገሩ እዬተነጠሉ ይታረዳሉ፤ ይደፈራሉ፤ ወንዶችም ይሰለባሉ – ይደፈራሉም፤ በፍል ይቀቀላሉ፤ በፎቅ ይፈጠፈጣሉ። በገጀሞ ይከተከታሉ —- ይታረሳሉ፤ ቄንጠኛው ደግሞ ዳንሱን እንዲህ ያስነኩታል ….

አዎን! በሺህ የሚቀጠሩ ዜጎቻችን ዜግነታቸው የትኛው ሊሆን እንደሚችልም መላ አጥተው ዛሬ ይታመሳሉ። የሱዳን ወይንስ የኢትዮጵያ? የሱዳን መንግሥትና የወያኔ የሽፍታ አስተዳደር የሚስጢሩ ድርድር „ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ ሆኗል።“ ቀንደኛው ሄሮድስ መለስ አፈር ሊያጫውቱ ቢሄዱሙም ጨፋሪው አቶ ሃይለማርያም ደግሞ በሙት መንፈስ ፈረስ እየጋለቡ ታሪክ ይቅር የማይለው አርበኝነትን፤ ታሪክን ማንነትን የዳጠ፤ የጠቀጠቀ ተግባር ፈጸሙ፤ ይንንም ሐሤት አድርገው የፍንጥሩን የልባቸውን ሞልተው የለ ምን ሲገዳቸው፤ እንዲህ ፍለቅልቅ ብለው ይደልቃሉ። በችርስ ይዘንጣሉ። ሳቅ በእናት ኢትዮጵያ ምድር ከገጠር እስከ ከተማ በፈለሰበት ዘመን ከሳቸው ቤት የበቀል ፈገግታ በገፍ እንዲህ ይመረታል – ወይ ነዶ! አሁን ዳንስስስስስ! ህም!

ሚሊዮኖች አስፓልትን ተጠልለው ነገን በሞት ይጠባበቃሉ። የኑሮ ዋስትና፤ የጤና ዋስትን፤ የመማር ዋስትና የላቸውም። የዕምነት አዛውንቶች ካለ ባህላቸውና ትውፊታቸው ስደትን የሙጡኝ ብለው እንደከሰሉ ያልፋሉ። ሀገርም ያሉት የጸሎት ቤታቸው በስጋት ተወጥሮ ከሞቱት በላይ ካሉት በታች ሆነው ተሳቀው ይኖራሉ። ዳንሰኛውም ደግሞ ዳንኪራቸውን እንዲህ መሬት አይበቃኝ ብለው መድረኩን ቀውጢ አድርገው ያስነኩታል …. ፍርሰት —

ለእለት ጥም ጠብታ ማርኪያ የሚማስኑ ዕልፎች ናቸው። እንደተቆለፈባቸው ጧሪና ጠያቂ አጥተው ትውልዱን ረግመው የሚሰናበቱንም እጅግ በርካታ ናቸው። ቄንጠኛው ዳንሰኛ አቶ ሀይለማርያም ደግሞ ሞቅ ብሏቸው፤ ጥጋቡም አላስችል ብሏቸው እንዲህ ይሉታል …. ማላጋጥ … ምልገትም —-
tedrows
ጠቀራ የለበሱ ቀናት ረሃብን እያወጁ፤ ስጋትን ነጋሪት እዬጎሰሙ፤ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ጎጆ እንደ ጉድ ይተማሉ። ቅብጠት ያመራቸውና ያልወጣላቸውም ጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማርያም ደሳለኝ ደግሞ ክርስትናውን ባፍ ጢሙ ብለው ይደልቁታል። ሁሉም አይቅርብኝ በማለት ከተቃራኒ ፆታ ጋርም የዐይን ፍሰቱንም ሆነ የእግር ዳንኪራውም እንዲሁም የመንፈስ ኮማውም …. በአንድነት በመደዴ ያስኬዱታል —- እርግማን!

አሁን ያን የሳውዲ ሰቆቃ ያዬ ፍጡር ዳንስ? ፈንጠዝያ?! ውቂ ደብልቂ?! እፍረት ነው። እውነት ለከፈን፤ ለመጠለያ፤ ለጉሮሮ ያልበቃች በብድር የተነከረች ሀገር እዬመሩ እንዲህ ሃላፊነት የጎደለው የአደባባይ ጥቁር ትዕይንት ማሳዬት እጅግ አንገት ያስደፋል ህሊና ላለው ሰው። „ባልወለድ“ ማለት የነበረበችው እርሳቸው ነበሩ ግን … በዬትኛው ህሊና?

ለነገሩ ምን አለባቸው እሳቸው አልጎደለባቸው። ፈሰስ ብለው ይኖራሉ። እልፎች ድምጻቸው ታፍኖ መተንፈስ ሲጀምሩ እዬተለቀሙ ለእግር ብረት ይዳረጋሉ። ልጆች ካለወላጅ፤ ጎጆም ካለ ጉልቻ፤ ትውልድም በነጠፈ ተስፋ 23ዓመት እንደዋዛ … ወገን ደም እንባ እያለቀሰ ታፍኖ፤ ተከዝኖ የሞት ቀናትን ይጠብቃል። ናፍቆት እስክንድርና መሰሎቹ ህጻናት ደግሞ ወላጆቻቸውን ተነጥቀው በሰው ሀገር ናፍቆታቸውን ሰንቀው ባልበሉት እዳ ይታሻሉ። ክልትምትም ይላሉ። አቶ ሃይለማርያም ደግሞ ከመላ ቤተሰባቸው ጋር የልጆቻቸውን ፍቅር ጠዋት ማታ እዬኮመኮሙ ጥጋቡ አላስችል ብሏቸው እንዲህ በመከራ ላይ፤ በግፍ ላይ ይጨፍራሉ ትዝብት ነው ….

ክውና — እረኛ ያጣ ህዝብ፤ ሙሴ የሌለው ትውልድ፤ ባላቤት የሌላት ኢትዮጵያ በፈላ እንባ እስከ መቼ ይሆን መቀቀሉን የሚቀጥሉት? ፈጠሪ አምላክስ መቼ ነው ፍርዱን አደላድሎ በቃችሁን የሚያውጅው!?! ….. ለግፍኞች፤ በእንባ ጨፋሪዎችስ ላይ ቅጣቱን አከታትሎ መቼ ነው የዶግ አመድ አድርጎ ብን የሚያደርጋቸው …. ? መቼስ „ተስፋ“ አያልቅ ደግሞ እንደ አመላችን „ተስፋ“ የሚባለውን እንጠብቅ ወይንስ ከእሱ ከራሱ „ተስፋ“ ከሚባለው ልብ አንጠልጣይ ጉድ ጋር ጦርነት እንግጠም ይሆን?

በሉ የኔዎቹ በዚህች ቆራጣ መጣጥፍ ትንፋሽ — የውስጤን ቁስለት በማሳዬት ተብተከትኩ። ለነበርን መልካም ጊዜ አመሰገንኩ – በፍቅር። ደህና ሰንብቱ።

እልፍ ነን። እልፍነታችን በተግባር እልፍ እናድርገው።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

[ውንብድና ካርቱም በሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ] –ሁዳ የሚባል እስር ቤት 35 ጠያቂ የሌላቸው እስረኞች ይማቅቃሉ

$
0
0

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ

በዓለም ዉድድር አለ። ዉድድሩ በህዝቦች መካከል ነው። ህዝቦች ዉድድሩን ለማሸነፍ አብሮነትን ይፈልጋሉ። በአብሮነት የራሳቸው ደህንነትና ጥቅም ማስከበር ይሻሉ። ደህንነታቸውንና ጥቅማቸው ለማስከበር ሀገር ይመሰርታሉ። ሀገር መስርተው በመንግስት ይወከላሉ። የመንግስት ተግባር ታድያ የህዝቡን ጥቅምና ደህንነት መጠበቅ ነው። በዚሁ መሰረት መንግስት የህዝቦች ተወካይ ጠበቃ መሆን ይጠበቅበታል።

የህዝቦች ወኪል (ጠበቃ) ለመሆን መንግስት በተለያዩ ሀገሮች ኤምባሲ ይከፍታል። የኤምባሲው ሰራተኞች የሚወክሉትን ህዝብ ጥቅምና ደህንነት ይጠብቃሉ፣ ያስጠብቃሉ። ለዚሁ ተግባራቸው ሲባል ህዝብ ደሞዛቸውን ይከፍላቸዋል። ደሞዛቸው የሚከፈላቸው ከመንግስት ካዝና ነው። የመንግስት ገንዘብ የሚሰበሰበው ከህዝብ ነው፤ በግብር መልክ።

የካርቱም ከተማ ከፊል ገጽታ (ፎቶ ፋይል)

የካርቱም ከተማ ከፊል ገጽታ (ፎቶ ፋይል)


የኢትዮጵያ መንግስትም (መንግስት ልበለው) ከህዝብ ኪስ የሚከፈሉ የኤምባሲ ሰራተኞች አሉት። በተለያዩ ሀገሮች ያሉ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች በህዝብ ገንዘብ እየተዳደሩ የሚከፍላቸውን ህዝብ የሚበድሉ መሆናቸው እናውቃለን። ዛሬ ትኩረቴ የሳበ ግን በካርቱም ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ነው።

ካርቱም የሚገኙ ጓደኞቼ እንደላኩልኝ ከሆነ የኢትዮጵያ ኤምባሲ (በካርቱም) ሰራተኞች በሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ተግባር ተሰማርተው ኢትዮጵያውያንን አደጋ ዉስጥ እየጣሉ ይገኛሉ። የሰዎች ደህንነት ከመጠበቅ ይልቅ ሰዎችን አደጋ ዉስጥ ማስገባት ምን ይሉታል? የመንግስት አካላት ወንጀልን ከመከላከል ይልቅ ቁማርተኞች ሲሆኑ ምን ማድረግ ይቻላል?!

የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች ሱዳን ዉስጥ የሚቸገሩ ዜጎቻችንን ደህንነት ከመከታተል ይልቅ ከሱዳን መንግስት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያውያን እስርቤት ይከታሉ። እስካሁን ድረስ በሱዳን ብዙ ኢትዮጵያውያን ያለ ምንም ጠያቂ በወህኒቤቶች እየማቀቁ ነው። የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች በሱዳን ሀገር የሚደርስባቸው ችግር፣ እስር፣ እንግልት እያወቁ በሰዎች ንግድ መሰማራታቸው ይገርማል። የኤምባሲው ሰራተኞች በሀገራቸው ሰዎች ንግድ ነው የተሰማሩ።

በሱዳን ያሉ ኢትዮጵያውያን መንግስት እንደሌላቸው (መንግስት አልባ እንደሆኑ) ነው የሚቆጠረው። “ሑዳ” በሚባል ወህኒቤት 35 ጠያቂ የሌላቸው ኢትዮጵያውያን አሉ። እነዚህ እስረኞች ያለ ምንም የፍርድቤት ዉሳኔ የተያዙና ከ8-12 ዓመት በወህኒቤቱ የቆዩ ናቸው። ተሰቅለው የተገደሉም መዓት ናቸው። በሱዳን የኢትዮጵያውያን ህይወት ርካሽ ነው። መስከረም አያሌው የተባለችም በሰባት ሱዳናውያን መደፈሯ ይታወሳል።

ኢትዮጵያውያን መንግስት አልባ (stateless) ሁነው ሲሰቃዩ የኤምባሲው ሰራተኞች ግን ሰዎች እየገዙና እየሸጡ (በሰዎች ንግድ ተሰማርተው) ገንዘብ ይሰበስባሉ። ዘመናዊ መንግስታዊ የንግድ ባርያ መሆኑ ነው።

ኢትዮጵያውያን ክብራችንን የምናስመልስበት ግዜ ሩቅ አይሆንም። አቶ መሐመድ ቱፋና አቶ በላቸው ግን ተግባራቹሁ ሁሉ እየተከታተልነው እንገኛለን።

Health: ስለ ኩላሊት ጠጠር ሊያውቁ የሚገባዎት 5 ነገሮች

$
0
0

ከማስረሻ መሐመድ

የኩላሊት ጠጠር የሚባሉት አብዛኛውን ጊዜ የካልስየም ክሪስትያል የሚሠሯቸው ድንጋዮች ሲሆኑ በኩላሊት ውስጥ የሽንት መጠራቀሚያ ቦታ ላይ የሚፈጠሩም ናቸው፡፡ ይህ ጠጠር መሠል ባዕድ ነገር ብዙ ጊዜ ባለበት ቦታ ላይ ችግርን የሚፈጥር ሳይሆን ሆኖም ግን የሽንት ቧንቧ ላይና ወደ ሌሎች አካላቶች ላይ መግባት ሲጀምር ችግር እየፈጠረ እንደሚመጣ በዘርፉ ያሉ ባለሞያዎች ይገልፃሉ፡፡

ኩላሊት ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ በሰውነታችን ውስጥ የሚያስፈልጉ ነገሮችን ከደም እያጣራ በሽንት መልክ ማስወገድ ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ታዲያ አንዳንድ ሚኒራልና ኬሚካሎች ኩላሊት ውስጥ በመቅረት ወደ አሸዋነት ይቀየራሉ፡፡ ከጊዜ በኋላም እነዚህ አሸዋ መሰል ነገሮች ወደ ድንጋይ
በመቀየር አደጋን ያስከትላሉ ማለት ነው፡፡

Kidney stone
1ኛ. የኩላሊት ጠጠር ለምን ይከሠታል?

የኩላሊት ጠጠር በአንዳንድ ሰዎች ላይ በምን አማካኝነት ሊከሠት እንደሚችል የተረጋገጠ ነገር የለም በአንዳንዶች ላይ ደግሞ በምን እንደተከሰተ ማወቅ የሚቻልበት ደረጃ እንዳለ ባለሞያዎቹ ያስረዳሉ፡፡ ይሁንና ከላይ እንደጠቀስነው ኩላሊት ደምን ሲያጣራ በሚቀሩ ሚኒራሎችና ሌሎች
ጠጠር ነገሮች አማካኝነት ሊከሰት እንደሚችል ነው፡፡

2ኛ. የኩላሉት ጠጠር ተጋለጮች እነማን ናቸው?

• ከ8ዐ በመቶ በላይ የሚሆነው የኩላሊት ጠጠር ተጠቂ ወንዶች ናቸው፡፡
• በዘር አማካኝነት ሊተላለፍ እንደሚችልም ይነገራል በተለይ እንደ ሲስታይን፣ኦክስሬት እና ዩሪክ አሲድ የመሳሰሉ ኬሚካሎችን ሜታቦላይዝ ማድረግ ኩላሊት ካልቻለ፡፡
• ሞቃታማ አካባቢ የሚኖሩና ፈሳሽ አዘውትረው የማይወስዱ ሰዎች ላይ ይከሠታል፡፡
• የካልሲየምና የቫይታሚን ዲ ንጥረ ነገሮችን አብዝቶ መጠቀም፡፡
• በብዛት መድኃኒቶችን መጠቀም በተለይ ዲላቲን፣ሴፋትራክሶን እንዲሁም ሲፕሮፋሎ ክሳስሊን የተሰኙ መድኃኒቶችን በበለጠ የኩላሊት ጠጠርን ያመጣሉ፡፡
• በደማቸው ውስጥ የኤች.አይ. ቪ.ቫይረስ ያለባቸው ሰዎችም ተጋላጮች ናቸው፡፡

3ኛ. የኩላሊት ጠጠር ምልክቶች

የኩላሊት ጠጠር በተለይ በኩላሊት ላይ ብቻ ተቀምጦ ከቆየ ምልክቶችን በአብዛኛው አያሳይም ይሁንና ይህ ሁኔታ ለከባድ ኢንፌክሽን ሊዳርግ ይችላል፡፡ ይህ ጠጠር ታዲያ ከኩላሊት ወደ ፊኛ መተላለፍ ከጀመረ ቶሎ ቶሎ መሽናት እና የሽንት ግፊት መጨመር ያስከትላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የጎን ውጋት መራቢያ አካላት ላይ ከፍተኛ የማቃጠል ስሜት እንዲሁም ውጋት መሠል ህመም፣ ማቅለሽለሽ፣ ማስመለስ፣ በሽንት ላይ ደም መታየት ዋናዎቹ ናቸው፡፡

4ኛ. የኩላሊት ጠጠርን እንዴት ማከም ይቻላል?

የኩላሊት ጠጠር ያለባቸው ህሙማኖችን ለመለየት ሐኪሞቹ በቀላሉ በሚያዩት ምልክት ለይተው ማከም ይችላሉ፡፡ ከዚህ በተረፈ ግን ለህክምና የሚውሉ መሣሪያዎች ማለትም እንደ ኮምፒዩተራይዝድ ቴሞ ግራፊ /CT/ እንዲሁም በአልትራሳውንድ አማካኝነት ጠጠሩ እንዳለ ማወቅ ይቻላል፡፡ በአብዛኛው የኩላሊት ጠጠር በራሱ የሚወጣ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህም የሚሆነው አብዝቶ ውኃ ፈሳሽን በመውሰድ ነው፡፡ አንድ የኩላሊት ጠጠር በኩላሊቱ የተገኘበት ሰው በቀን ሁለት ሊትር ውኃ ቢጠጣ ጠጠሩን ጨርሶ ሊያስወግደው ይችላል፡፡ ከዚህ ካለፈ ግን ሌላው አማራጭ ቀላል ቀዶ ጥገና በማድረግ ጠጠሩን የማስወገድ ስራ ነው፡፡ ይህ ታዲያ በህክምና ባለሞያዎች የሚከናወን ነው፡፡

5ኛ. የኩላሊት ጠጠርን መከላከል ይቻላል?

የኩላሊት ጠጠርን ለመከላከል ወይም እንዳይከሰት ለማድረግ በየቀኑ ሁለት ሌትርና ከዛ በላይ ውኃ መጠጣት አስፈላጊ ነው፡፡ ሆኖም ግን በተለይ በመድኃኒት ለሚመጡ የኩላሊት ጠጠሮች አሁንም አብዝቶ ፈሳሾችን በመውሰድ ቶሎ ቶሎ እንዲሸኑ ስለሚያደርግ በዚያም አማካኝነት ጠጠሩን ማውጣት ስለሚቻል ፈሳሹን መውሰድ ጠቃሚ ነው፡፡

እንግዲህ የኩላሊት ጠጠር እኛ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ሌሎች አለም ላይ ያሉ ህዝቦችን ከአንዱ አንዱን ሳይለይ የሚያጠቃ የበሽታ አይነት ነው፡፡ ሆኖም በሽታውን በቀላሉ መከላከል እንደሚቻል ከላይ ለማስቀመጥ ሞክረናል፡፡ ስለዚህ ያንን በመጠቀም በሽታውን በቀላሉ መከላከል ነው፡፡ አልያም ደግሞ በአቅራቢያዎ በሚገኙ የህክምና መስጫ ተቋማት በመሄድ ስለበሽታው መረዳት መልካም ነው እንላለን፡፡ ቸር እንሰንብት፡፡

“የኦነግ ጭፍጨፋ ተብለው ከሚጠቀሱ ትራጄዲዎች መካከል አብዛኛዎቹ በኦነግ የተፈጸሙ አልነበሩም”–ከአፈንዲ ሙተቂ

$
0
0

olf flag
ከአፈንዲ ሙተቂ

——
“ዳውድ ኢብሳ ሲሞት ጥሩኝ” በሚል ርዕስ በለጠፍኩት አነስተኛ ሐተታ ላይ ሁለት ዓይነት ተቃውሞዎች ቀርበውብኛል፡፡ አንደኛው “ኦነግ በአማራው ላይ የሰራውን ሴራ እና ሸፍጥ እያወቅክ ጥብቅና ቆመህለታል” የሚለው ሲሆን ሁለተኛው “የኦፒዲኦን ድርጅታዊ ህልውና አንኳሰስክ፤ አቶ አለማየሁንም ረገጥክ” የሚል ነው፡፡ ስለ ኦፒዲኦ የጻፍኩት አዲስ ነገር አይደለም፡፡ የድርጅቱ አባላት እራሳቸው በየአጋጣሚው የሚናገሩትን ነው በፌስቡክ የደገምኩት፡፡ በተለይ ደግሞ አባላቱ ከስራቸው ሲባረሩ፣ ወይ ደግሞ ከድርጅቱ ከድተው ወደ ውጪ ሀገር ሲኮበልሉ “ኦፒዲኦ የኦሮሞን ህዝብ ለማጭበርበር ሆን ተብሎ የተፈጠረ ድርጅት ነው” የሚል ጩኸት በማሰማት ነው የሚታወቁት፡፡ እነ ዮናታን ዲቢሳ፣ ዱባለ ጃሌ፣ ኢብራሂም መልካ ሲያደርጉት የነበረው ይህንኑ ነው፡፡ ነገር ግን እኔ የነርሱን ፈለግ በመከተል አይደለም እንዲያ ብዬ የጻፍኩት፡፡ ከነርሱ በፊትም እንደዚያ ስል ነበር፡፡
——
ኦነግን ለመጀመሪያ ጊዜ ካየሁበት ግንቦት 1983 ጀምሮ የድርጅቱን የፖለቲካ መስመር ስደግፍ ቆይቻለሁ፡፡ ዩኒቨርሲቲ ስገባ ግን ድርጅቱ በሚያራምደው ርዕዮተ ዓለምና በፖለቲካ ፕሮግራሙ ላይ ጥያቄዎች ማንሳት ጀመርኩ፡፡ በዋነኛነትም “የመገንጠል ፖለቲካው የኦሮሞን ጥያቄ የትም አያደርሰውም” የሚል ሀሳብ አነሳሁ፡፡ እንዲሁም የሚከተላቸው ስትራቴጂዎቹ ፍጹም ሊዋጡልኝ አልቻሉም፡፡ በዚህም ከኦሮሞ ወንድሞቼ ጋር ብዙ ጊዜ እነታረክ ነበር፡፡ በተለይም በዚያ ጊዜ ኦነግን መተቸት Taboo ተደርጎ ይቆጠር ስለነበር ከቅርብ ጓደኞቼ ጭምር እስከመጣላት ደርሰናል፡፡ እናም ከ1990 ጀምሮ የድርጅቱ ተቃራኒ እንጂ ደጋፊ አይደለሁም፡፡

እንዲህ በመሆኑ ግን ድርጅቱን በሐሰት መክሰስ ያለብኝ አይመስለኝም፡፡ ድርጅቱን በሰራው ጥፋት ብወቅሰው ማለፊያ ነው፡፡ ባልሰራው ወንጀል መክሰስ ግን ለማንም የሚበጅ አይሆንም፡፡ እንደምሳሌም ኦነግ የሚከሰስባቸውን ጭፍጨፋዎች እንመልከት፡፡ በደኖ፣ አርባ ጉጉ፣ ወተር፣ አረካ፣ አሰቦት ገዳም ወዘተ…

እነዚህ ጭፍጨፋዎች መከሰታቸው ሁላችንንም ያሳዝነናል፡፡ አንድ ቀን እውነቱን ፈልፍለን የማውጣት ግዴታም ተጥሎብናል፡፡፡ ነገር ግን በርካታ ሰዎች በሁሉም ጭፍጨፋዎች ኦነግን ተጠያቂ ሲያደርጉ በጣም እገረማለሁ፡፡ በተለይም ዛሬ በህትመት ላይ የሌሉ ሁለት የግል ጋዜጦች ይህንን ፕሮፓጋንዳ እየደጋገሙ ሲያስተጋቡት ሳይ “ስለ የትኛው ሀገር ነው የሚያወሩት” እያልኩ እደነቅባቸው ነበር፡፡ እንዲህ የምለው ጋዜጦቹ የመረጃ እጥረት የነበራቸው መሆኑን በማወቄ ብቻ አይደለም፤ የጂኦግራፊ እውቀትም ያጠራቸው ስለሚመስለኝም ጭምር ነው፡፡ ለምሳሌ “አረካ”ን እንውሰድ፡፡ ይህቺ ከተማ የት ነው ያለችው? ኦሮሚያ ውስጥ ነው? ወይስ ሌላ ቦታ?

ይገርማል! አረካ ማለት በደቡብ ክልል በወላይታ አውራጃ ከሶዶ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ ያለች ከተማ ናት፡፡ እኔ እስከማውቀው ድረስ ኦነግ እዚያ ድረስ ሄዶ ሀገር አላስተዳደረም፡፡ “አረካ የኦሮሚያ ግዛት ናት” ብሎ የሚያውቅም አይመስለኝም፡፡ እናም ጂኦግራፊን በትክክል የሚያውቅ ጋዜጠኛ የአረካውን ግጭትና ጭፍጨፋ ለኦነግ አይሰጥም ነበር፡፡ በተጨማሪም የአረካው ግጭት የደረሰው ኦነግ የሽግግር መንግሥቱን ለቆ ከወጣና በእጁ የነበሩት መሬቶች በሙሉ በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር ከወደቁ በኋላ ነው፡፡

የአረካው ግጭት በሽግግሩ ዘመን ለነበረው የተወካዮች ምክር ቤት የውይይት አጀንዳ ሆኖ እንደቀረበ ይታወሳል፡፡ በከተማዋ ያለቁት የ31 ሰዎች ግድያ በመከላከያ ሰራዊቱ እንደተፈጸመ መንግሥቱ በይፋ አምኗል፡፡ ዳሩ ግን ለግድያው የተሰጠው ምክንያት በጣም አነጋጋሪ ነበር፡፡ መንግሥት ያቀረበው ምክንያት “ሰልፈኞቹ የተገደሉት ቦንብ በመወርወራቸው ሳቢያ የመከላከያ ሰራዊቱ ራሱን ለመከላከል በወሰደው እርምጃ ነው” የሚል ነው፡፡ ይሁንና ይህንን ምክንያት ብዙዎች አልተቀበሉትም፡፡ ብዙዎች እንደተጠራጠሩት እስከ ዛሬ ድረስ ቆይቷል፡፡ በነገራችን ላይ በአረካ የሞቱት የቀድሞ መንግሥት ወታደሮች ነበሩ፡፡ እነዚያ ወታደሮች “የጡረታ መብታችን ይከበርልን” በማለት የተቃውሞ ሰልፍ በማድረጋቸው ነው ከመከላከያ ሰራዊቱ ጋር የተጋጩት፡፡
——–
በሚያዚያ ወር 1984 በወተር ከተማ በተካሄደ ጭፍጨፋ የሞቱትም በተመሳሳይ መልኩ በመከላከያ ሰራዊቱ እንደተገደሉ የሽግግር መንግሥቱ በወቅቱ አምኗል፡፡ ይሁን እንጂ በወተር የተገደሉት 230 ሰዎች በሙሉ ኦሮሞዎች እንጂ አማራዎች አልነበሩም፡፡ እነዚያ ሰዎች የተገደሉት ኢህአዴግ ከከተማቸው ወጥቶ ኦነግ ወደ ከተማዋ እንዲመለስ በመጠየቃቸው ነው (ወተር ለአንድ ዓመት ያህል በኦነግ ቁጥጥር ስር ነበረች፤ ኦነግ ከከተማዋ ሲወጣ ኢህአዴግ ገብቶባታል፤ ነዋሪዎቹ “እንደ ቀድሞው ጊዜያችን ኦነግ ወደ ከተማዋ ይመለስ” በማለታቸው ነው ከመከላከያ ሰራዊቱ ጋር የተጋጩት)፡፡ ጋዜጦቹ ግን “ኦነግ አማራዎችን ጨፈጨፈ” እያሉ ነበር የሚዘግቡት፡፡
——-
በ1984 (ወሩን አላስታውሰውም) በአሰቦት ገዳም በተካሄደ ግድያ ሰባት መነኮሳት ሞተዋል፡፡ ይህንን ግድያ የፈጸሙትም በወቅቱ የአሰቦት ከተማን ለትንሽ ጊዜ ተቆጣጥሮ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት እስላማዊ ግንባር (IFLO) ታጣቂዎች ነበሩ፡፡ ግድያው ስር ሳይሰድ በአፋጣኝ ያስቆሙት ደግሞ ኢህአዴግና ኦነግ ነበሩ፡፡ ሁለቱ ድርጅቶች አንድ ጥምር ኮሚቴ በማቋቋም በወሰኑት ውሳኔ መሰረት IFLO ከከተማው ተባርሮ አካባቢው በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል፡፡
——
በአርባ ጉጉ የተፈጸመው እልቂት በሁለት ተጎራባች መንደሮች መካከል በተካሄደ ግጭት ነበር የተለኮሰው፡፡ እያደር ግን መርቲ ጀጁ እና አሰኮ የሚባሉ የአርባ ጉጉ ወረዳዎችን አዳርሷል፡፡ በግጭቱ የኦሮሞ እና የአማራ ተወላጆች በእኩል ደረጃ ተጎድተዋል፡፡

በአርባ ጉጉ ግጭት የራሳቸውን የፖለቲካ ትርፍ ለማጋበስ የፈለጉ ወገኖች እጃቸውን አስገብተውበታል ይባላል፡፡ በመሆኑም በውጤቱ ከሁሉም ግጭቶች የከፋ ሊሆን ችሏል፡፡ በዚህ ግጭት ከሁለቱም ወገን እስከ ስድስት መቶ ያህል ሰዎች መሞታቸው ይነገራል፡፡ ከመቶ ሺህ ያላነሰ ሰው ወደ ሀረርጌና ሸዋ ክፍለ ሀገሮች ተፈናቅሏል፡፡ ሆኖም ኦነግ በዚህ ግጭት ውስጥ እጁን ማስገባቱን የሚያረጋግጥ ፍንጭ እስከ አሁን ድረስ የለም፡፡ ኦነግ በወቅቱ በአርባ ጉጉ አውራጃ ምንም ይዞታ አልነበረውም፡፡ የመላው አማራ ህዝብ ድርጅትም ቢሆን በግጭቱ የከሰሰው ኦህዴድን (OPDO) እንጂ ኦነግን አልነበረም፡፡ በተለይም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የምዕራብ ሸዋ ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ የነበረው ኮሎኔል ዲማ ጉርሜሳ ከግጭቱ ጋር ተያይዞ ስሙ በሰፊው ይነሳ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ በዚያን ጊዜ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ሐሰን ዓሊ ከእፎይታ መጽሔት ጋር (ግንቦት 1985) ባደረጉት ቃለ-ምልልስ “አቶ ዲማ ጉርሜሳ ንጹሕ ነው” በማለት ከመከላከላቸውም በላይ ለግጭቱ ዋነኛ ተጠያቂ ያደረጉት መአሕድን እንጂ ኦነግን አልነበረም፡፡

የግል ጋዜጦች ግን ነገሩን አራግበው በኦነግ ላይ አላከኩት፡፡ ነገሩን ሳያውቁት ቀርተው የተደረገ አይመስለኝም፡፡ አንዳንድ ጋዜጦች -ተከፍሎአቸው እንዲህ እንደሚያደርጉ በደንብ እናውቃለን፡፡
——–
የበደኖ ጭፍጨፋ! አዎን! ኦነግ ሊጠየቅበት የሚገባው ብቸኛው ትራጄዲ ይህኛው ነው፡፡ በርግጥም እልቂቱ በተፈጸመበት ወቅት በደኖ በኦነግ ቁጥጥር ስር ነበረች፡፡ የሞቱት ሀምሳ ያህል ሰዎች ለምን እንደተገደሉ ባይታወቅም አድራጎቱ በኦነግ ወታደሮች እንደተፈጸመ ድርጅቱ ራሱ አምኗል፡፡ ኦነግ በወቅቱ በወታደሮቹና በአዛዦቹ ላይ እርምጃ ወስጃለሁ ቢልም የተወሰደውን እርምጃ ምንነት አልገለጸም፡፡ በነገራችን ላይ በዚህኛውም እልቂት ከሞቱት መካከል ግማሽ ያህሉ ኦሮሞዎች ነበሩ፡፡
—–
ከላይ በዝርዝር እንዳስረዳሁት የኦነግ ጭፍጨፋ ተብለው ከሚጠቀሱ ትራጄዲዎች መካከል አብዛኛዎቹ በኦነግ የተፈጸሙ አልነበሩም፡፡ ኦነግ ሊጠየቅበት የሚገባው ብቸኛው ድርጊት በበደኖ የተፈጸመው ነው፡፡ የእውነት ቀን ሲመጣ ያንን ፋይል ማውጣታችንም አይቀሬ ነው፡፡ ይሁንና በኦነግ ያልተፈጸመውን ከርሱ ጋር አያይዞ መጻፍ ጥቅሙ ምን እንደሆነ ሊገባኝ አይችልም፡፡ እንዲያውም የያኔዎቹ የግል ጋዜጦች የሚያራግቡት ወሬ በተወሰነ መልኩ የኦነግ ጨካኝነትን ከመግለጽ ይልቅ “ኦሮሞ ጨካኝ ነው” የሚል እድምታ ለመፍጠር የታለመ ነበር የሚመስለው፡፡

እርግጥ የኦነግ ወታደሮች በብዙ አጋጣሚዎች ልዩ ልዩ የጭካኔ ተግባራትን ሲፈጽሙ ተስተውለዋል፡፡ እርሱን አንክድም፡፡ የነርሱ ገፈት ቀማሽ ሆኖ የዘለቀው ግን በአብዛኛው ኦሮሞው ነው እንጂ የሌላ ብሄረሰብ ተወላጅ አልነበረም፡፡ በተለይ አንዳንዶቹ የኦነግ ወታደሮች “ጎበና፤ ቢተምቱ.፤ ወዘተ..” ለሚሏቸው ግለሰቦች ምህረት አልነበራቸውም፡፡ እንዲሁም ተጻራሪ ድርጅት ሊያቋቁሙ ነው በሚል ፍርሃት አባላቶቻቸውን ጭምር እስከ መግደል ይደርሱ ነበር (የኦነግ የሀረር ቢሮ ሃላፊ የነበሩትን አቶ አራርሶ ወዳይን እና በመቻራ ከተማ የተገደለውን የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ካሊድ ሃጂ ኑራን መጥቀሱ ይበቃል)፡፡ ሆኖም ጋዜጦቻችን ድርጅቱ የፈጸመውን ማውራት ይተውና ድርጅቱ ያልፈጸመውን ወንጀል ይነግሩን ነበር! ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ማለት ይህ ነው፡፡

ለማጠቃለል ያህል እኔ ለኦነግ አልተከላከልኩለትም፡፡ አንዳች ጥብቅና አልቆምኩለትም፡፡ የጻፍኩት የማውቀውን ሐቅና የማምንበትን አቋሜን ነው፡፡ ይሁንና ይህ አባባሌ ኦነግን ከመፍራት እንዳይወሰድብኝ አደራ እላለሁ! አስፈላጊ ከሆነ በኦነግም የተፈጸሙ ስህተቶችና ጥፋቶችን አንድ በአንድ መዘርዘር እችላለሁ፡፡

ሰናይ ቀን ይሁንላችሁ!!


ያረጋገጥነው የምግብ ኢዋስትናን (ዋስትና አላልኩም) ነው።

$
0
0

ከሠሎሞን ታምሩ ዓየለ
ክፍል 4
በክፍል 3 መጣጥፌ በዋናነት የአገራችን የተፈጥሮ ሃብቶችና ዓየር ንብረቷም ለተለያዩ አዝርዕቶችና ኦንስሳቶች ልማት ምቹነቱን በመግለጽ ነበር ያቆምኩት። አሁን በሚቀጥለው ደግሞ በክፍል 2ት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያልቻልንባቸውን መሠረታዊ ተግዳርቶች ውስጥ እንደ መንስኤ የቆጠርነው የመንግስትን በተለይም የአምባ ገነንነት ቅርጽ የያዙት የሚከተሉት ያልተስተካከለ የግብርና ፖሊሲ ተወግዶ በምትኩም ትክክለኛውና ለውጥ ሊያመጣ የሚችለው የግብርና ፖሊሲና ስትራቴጂ ምንን ማዕቀፍ ማድረግ እንዳለበት የአቅሜን ያህል ለማሳዬት ነው።
እንዲህ ልጀምር። በፖሊሲ ጥየቄና ዝግጅት የተለየ ትምህርት ወይም ሥልጠና የለኝም። ፖለቲከኞች፤ የመንግስት ሹማምንቶች፤ ኢኮኖሚስቶች፤ ለሎችም የማኀበራዊ ሳይንስ ሰዎችና በስፋትም በትልልቅ ኮርፖሬሽኖችና ካምፓኒዎችም ውስጥ ቃሉ ተደጋግሞ ይደመጣል። እኔም ከጊዜ ብዛት ትንሽ የገባችኝን ያህል ላክልባት። ” መወያየት መልካም” የሚል አብዮቱ ከመፈንዳቱ በፊት በኢትዮጵያ ሬዲዮ ፕሮግራም እንደ ነበር ትዝ ይለኛልና ያንን መሰረት በማድረግ ልቀጥል። የአገሬ የፖሊሲ ማውጣት ስራዎች እንዴት እንደሚዘጋጁና እንደሚጠናቀቁ፤ ዋነኛ ተቋሞቹ የት የት እንደሚገኙ ግን ለአብዛኛው ኢትዮጵያዊ እኔንም ጨምሮ የምናውቀው አይመስለኝም ( ምን አልባት መንግስት ጓዳ ይሆን)። ለመሆኑ ፖሊሲ ምንድነው? ፖሊሲ ሃሳብ፤ መርህ፤ አቅጣጫ፤ ሥርአት፤ መንገድና መመሪያ ነው ብል ትልቅ ስህተት የሰራሁ አይመስለኝም። ባጭሩ ፖሊሲ በህግ፤ በአዋጅ፤ በደንብ ፤ በትዕዛዝ፤ በመመሪያና በአሰራር ተደግፎ ወደ ተግባር ለመለወጥ ይመነዘራል። የፖሊሲ ምንጩ ወይም መነሻው ችግር ነው ቢባልም ማጋነን አይሆንም። የችግሩ አብዛኛውን ጊዜ ሰለባ ወይም ተጠቂ ደግሞ ሕዝብ ነው። ስለዚህ እውነተኛና ሕዝባዊ ፖሊሲ የሕዝብን የልብ ትርታ (አመታት በህክምና ሰዎች ቋንቋ) አዳምጦና ተከትሎ የሚዘጋጅ ሰነድም ነው። ፖሊሲ አንዴ ከተነደፈ ችግር የለውም ማለትም አይደለም። እንደ አፈጻጸሙና አካሄዱ አመቺነት፤ እንደአስከተለው ችግር ቀላልነትና ግዝፈት ይለወጣል፤ በሌላም ይተካል፤ ይዳብራል፤ ይታደሳልም። መሠረቴና መኖሬ ለሕዝብ ነው ብሎ የተነሳ መንግሥት ደግሞ የፖሊሲውን ጥቅም ለሕዝብ አገልግሎት ቅድሚያ ይሰጣል። ፖሊሲው ሲነደፍ ከአሰራር ዝርክርክነት የጸዳና ለሚነሱ ጥያቄዎችም የጠራ መልስ የሚሰጥና ኃላፊነት፤ ተጠያቂነትና በሕዝብ ተአማኒነትና ተቀባይነት አንዲኖረው ያስፈልጋል። ለብዙሃን እንጂ መቆም ያለበት የጥቂቶችን ጥቅም ማስጠበቂያ መሳሪያ መሆን እንደሌለበት ዕሙን ነው። የአንድን አገር መሪ ቃል ብቻ ወይም የአንድን ፖለቲካ ፓርቲ የአቋም መስመር ተከትሎ እንደ መዘውር መንዳት የኋላ የኋላ ገደል ይዞ ይገባል። ባጭሩ ፖሊሲው የሕዝብ ፍላጎት መሆኑን በዚህኛው ወይም በሌላኛው ዘዴ ደህና አድርጎ ማረጋገጥ ይጠቅማል እንጂ አይጎዳም። የተዘጋጀው ፖሊሲ ሕዝባዊነት ከሌለው ደግም ተቀባይነቱና ተአማኒነቱ ይቀንሳል፤ ጭራሹንም ይጠፋል። የመንግስት ፖሊሲ ተቀባይነት የሚገመገመውም ለመንግስት ሹመኞችና ለቅርብ ባለስልጣናት በሚሰጠው ደስታና ፌሽታ ሳይሆን በሕዝብ ኑሮ ላይ በሚያመጣው አሉታው ወይም አዎንታዊ ገጹ እየታየ ነው። መንግስትም ይህንን ተገንዝቦ ያለመስማት ወይም ያለማዳመጥ ፖሊሲውን አዲዮስ ማለት አለበት። ምሁራን የሚሰጡትን ገንቢ አስተያዬት አሌ ማለት አይገባም። አንድ ወቅት ላይ በ1984 ዓም መሰለኝ ፕሮፌሰር መስፍን ኃ/ ማሪያም ከመንግስት ሰዎች ጋር እሰጥ እገባ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ለይ ጀምረው ሳለ እንዲህ እንዳሁኑ ነጻ ጋዜጦችና ድረ ገጾች ውድ በሆኑበት ጊዜ የሚከተለውን ተናግረው ነበር። “መንግስትና ምሁራን በኢትዮጵያ ሆድና ጀርባ ናቸው” ። በሃሳብም፤ በግብርም አልተገናኙም፤ አልተዋሃዱም ማለት ነው። ልጆች ሳለን ለሙሽሮች የምንዘፍነው ዘፈን ትዝ አለኝ። የሙሹሮችን መግጠምና መዋሃድ ለማብሰር እንዲህ በማለት ገጥመናል። እከሊትና እከሌ ምንና ምን ናቸው፤ የጆሮ ጉትቻ የአንገት ሃብል ናቸው። መንግሥትም ሕዝብ የኔ ነው ያላለውን ፖሊሲ ለማስፈጸም ደፋ ቀና ሲል ከሕዝብ ጋር ይጋጫል፤ ይቀያየማል፤ የተቃወሙትን በአደባባይ ይደበድባል፤ ያስራል፤ ይከሳልም፤ እስርም ይፈርዳል። ከፍ ካለ ደግም የጠመንጃ ቃታ ስቦ ደም ካፈሰሰ በኋላ በሰራው አስነዋሪ ሥራ ከተጠያቂነት ለማምለጥ በቁጥጥሩ ሥር ባደረጋቸው መገናኛ ብዙሃንን በመጠቀም “አንዳንድ የኅ/ሰቡን ሰላም ለማደፍረስ “ የሚል መግለጫ ይሰጣል፤ ይፎክራል፤ ያቅራራል ፤ ያስፈራራል። አንዳንዴም ሁኔታዎች አስጊ መሰሎ ከታየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያውጃል። ይህችን ፓራግራፍ በዚህች ጨዋታ ወይም ቀልድ ልቋጫት። አብሮኝ በአምቦ እርሻ ተቋም የተማረና በኢሉአባቦር ግብርና ተጠሪ ጽ/ ቤት በተለያዩ አውራጃዎችም ተመድበን ስንሰራ የነበረ ጉዋደኛ ነበረኝ። ጉዋደኛዬ ዕድገት በኅብረት (በእብደት ሳቅ!) የሥራና የዕውቀት ዘመቻ ከተሳተፉት ተማሪዎች አንዱ ነው። በምድብ ሸዋ በደንዲ ጣቢያ ያለኝ መሰለኝ። ታዲያ በ1968ንቱ አካባቢ በሱ መስመር ከወሎንኮሚ ጀምሮ እስከ ጌዴዎ ድረስ ያለው የጅባትና ሜጫ አርሶ አደር በሆነ ምክንያት ያምጽና በወቅቱ የሸዋው የደርጉ አንበሳ የነበሩቱ ኮሎኔል ደበላ ዲንሳን (ነፍስ ይማር) አመራር ለመከተል አስቸግሮ ኖሮ፤ ደበላ በላንድሮቨር፤ አጃቢዎቻቸው ደግሞ በፈጣኗ ከፍት ጂፕ ቢ አር መሣሪያቸው ተደቅኖባቸው ከተፍ ካሉ በኋላ፤ በየጣቢያው የሚገኘትን ዘማቾች ሰብስበው ዐመጹን ለማቆም ” ዘማቹ ተሜን “ መላ በሉኝ ብለው ስብሰባውን ለውይይት ይከፍታሉ አሉ። ተሜ ተንኮለኛዋ የምትሰጠው ሃሳቦች ሁሉ ያልተዋጠላቸው ደበላ በመጨረሻ እንዲህ አሉ ይባለል። እኔና ወታደሮቼ በምታይዋቸው ክፍት የጂፕ መኪናዎች ላይ የድምጽ ማጉያ ይዘን ከአዲስ ዓለም ጀምሮ እስከ ጌዴዎ ድረስ ባለው አውራ ጎዳና ላይ (አውራ ጎዳና ከተባለ በዛሬ መለኪያ) ” ሲ ዳጰና “ በአፋን ኦሮሚፋ እንዲሁም “ ላንተ ነው የቆምኩት “ ስለው ዓመጸኛው ሰጥ ለጥ ይላል ብለው አረፉት። አዎን! ሰላምና ሕዝባዊ ፖሊሲ ያለው አመራር ቅንና ደግ ነው። ለጊዜውም ቢሆን ጠመንጃንና ጉልበትን እንደ አማራጭ አልተጠቀሙም። በዚህ አጋጣሚ እኝህ ኢትዮጵያዊ የፖሊስ መኮንን ንግግራቸውና ምክራቸው ጣፋጭ መሆኗን በ1971 ዓም የአምቦ እርሻ ተቌም ምሩቃንን ሲመርቁ በአካል አይቻቸዋለሁኝ። አንዳንዶቹ ሰውዬውን ደህና አድርገው የሚያውቋቸው ደግሞ ቢዘገይም ቀይ ሽብር የተባለው ጸረ ወጣት፤ ጸረ ምሁርና ጸረ ተራማጅ ህይሎች እርምጃ በተለይ በሸዋ ጠ/ግዛት እንዲቆም ካደረጉት ውስጥ በዋናነት ይጠቅሷቸዋል።
በክፍል 2 መጣጥፌ የምግብ ዋስትናችንን ጉዳይ እንዳናረጋግጥ ካደረጉን ምክንያቶች አንዱ የሆነውን ተፈጥሮአዊ መንስኤ ጸባይ እንዳለው ገልጬ ነበር። አንዳንዶቹን ለመከላከልና ለመገደብ ብንሞክርም ሌላውን ግን ፈጣሪያችን ተፈጥሮን በቁጥጥሩ ሥር የሚያደርግ መሪ እስከሚሰጠን ድረስ በትዕግሥት እንጠብቅ። በሁለተኛው ምክንያት ላይ ግን የመሪዎቻችን መልካም ፍቃድ ለጊዜው ታክሎበት መስራት ይቻላል። ይሄ ነው ጥሩ ፖሊሲ ብሎም አፍን ሞልቶ ለመናገርም ሊቸግር ይችላል። ማውራት ሌላ፤ ስራ ሌላ አይደል። አዎን! መስራት እንደ ማውራት ቀላል አይዶለም። ነገር ግን በቅድሚያ የሚያሰራና የሚያንቀሳቅስ የግብርና ፖሊሲ ለማዘጋጀት ግን ያለንን የተለያየ ዕውቀት፤ ክህሎትና የስራ ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች በማቀናጀት በሃሳብ ነጻነት እንዲሰሩ ማድረግ የመልካም ግብርና ፖሊሲ የመጀመሪያው ምዕራፍ ፩ ሊሆን ይችላል። የዘመቻ ዓይነት አሠራር አስወግዶ በምትኩም ደህና አድርጎ በማሰብ የተዝጋጀ ፖሊሲ ያስፈልጋል። በሥራ ላይም ችግር ቢገጥመው ወዲያውኑ ሊስተካከል ይችላል። ስለዚህ በዚህ የግብርና ፖሊሲ ውስጥ እንዲካተቱ የምንፈልጋቸው ጉዳዮች በዋናነት የሚከተሉትን መሠረታው ጥያቄዎች ሊመልሱ የሚችሉ መሆን አለበት። ለምን? ማን? እንዴት? እንደምን? ምን? የት? የትኛው? መቼና ሌሎችንም ጥያቄዎች በማንሳት፤ የማይሰሩትን በማስወገድ ሃሳቡ ይጀምራል። በዚሁ ጉዳይ ብዙ አዋቂዎችና ምሁራን ተናግረዋል፤ መክረዋል፤ ዘክረዋል። መስማትና መተግበር ያቃታት ግን ይቺ መንግስት የሚሏት ተቋም ነች። እርሷ የምትፈልገው እኔን ብቻ አድምጡ፤ እኔ የምላችሁን ብቻ ደግፉ ነው። ፖሊሲው በግልጽ መሰረታዊ የሆነውን የመሬት ይዞታ ጥያቄ ካለማወላወል መልስ መስጠት የግድ ይለዋል። መሬት የግል ይዞታ ይሁን! የረዥም ጊዜ ጥያቄ መልስ ማግኘት አለበት። የደንና ዱር እንስሳትን ፤ የአፈርና የውሃ ሃብታችንን አጠቃቀም፤ አጠባባቅና አስተዳደር መፍትሄ ማበጀት አለበት። የመሬትን ዓይነት ምዘናና ምደባ በትክክለኛው፤ አግባብነትና ተቀባይነት ባለው መንገድ መዘጋጀት አለበት። የዘመናዊና ሰፋፊ ኣርሻዎችን ይዞታና የት የት ሥፍራ መሆን እንዳለባቸው በቅድሚያ ጥናት መሰረት አድርጎ መዘጋጀት ተገቢ ነው። የአካባቢ ነዋሪዎችንም ዕውቀት ከግምት ውስጥ ማስገባት ይጠቅማል እንጂ አይጎዳም። በተለይ በተለይ ደግም ከውጭ በኢንቨስትመንት ስም የሚያገኙትን የራሳቸውን ጥቅም ብቻ አስልተው የሚመጡትን ባለ ሃብቶች ክፉና በጎውን ለይተን ሳናጠና በችኮላ ፍቃድ መስጠት የኋላ የኋላ አገር ይጎዳል። ግልጽ የሆነና የትኞቹ የሰብልና የእንስሳት ዓይነቶች ቅድሚያ ትኩረትን ተችረው መልማት አለባቸው ተብሎ መጠየቅም አግባብነት አለው። የግጦሽ መሬት አጠቃቀምንና አያያዝን እንዲሻሻሉ መርሃ ድርጊት መንደፍ። የዓሳ ሃብታችንን በሳይንሳዊ ጥናት ላይ በተመረኮዘ አሰራር ማሻሻል። የምርት አያያዝን፤ አቀነባበርን፤ አዘገጃጀትንና ጥራት አጠባበቅን አዋጭውን መንገድ መከተል ። የምርት ዓይነቶች ተገቢውን የገበያ ዋጋ በጊዜና በቦታ እንዲያገኙና ሥርጭታቸውም የተስተካከለ እንዲሆን የአቅምን ያህል ካለ ማቋረጥ መጣር። ለገበያ የቀረቡ ምርቶችም የታክስ ዋጋ የማይጎዳ መሆኑን ማረጋገጥ ተገቢ ነው። የምርት ግብአቶች ሁሉ በተፈለው ጊዚና መጠን እንዲሁም ዋጋቸው የሚቻልና ተመጣጣኝ እንዲሆን መንግስት በጥናት ላይ የተመሠረት የዋጋ ድጎማ እንዲያደርግ አሠራሩን ማመቻቸትና ማስተካከል። ዋነኛ የሜካናይዝድ እርሻ አገልገሎት መስጫ ጣቢያዎች እንዲስፋፉና እንዲጎለብቱ ማበረታታት። የብድርና የባንክ አገልግሎቶችን በቅርበት እንዲገኙ አሰራሮችን ማሻሻልና ትኩረት ሰጥቶ መከታተል። የትምህርትና የሥልጠና መርሃ ፕሮግራማችንን በፍላጎትና በችግሮቻችን ዙሪያ በቅድሚያ ማዘጋጀትና መንደፍ፤ የምርምርና የሥርጸት ሥርአቱን ለስራው ምቹነት ባለው አካሄድ ማደራጀት። የልዩ ልዩ አገልግሎት መስጫ መዋቅሮችን ( መንገድ፤ ግድቦች፤ የመስኖ ቦዮች፤ ጎተራዎች፤ የሰው ሰራሽ እንስሳት ማዳቀያ ጣቢያዎችንና የእንሳሳት ህክምና መስጫ ክሊኒኮችን አርሶ አደሩ በቅርብ ርቀት የሚያገኝበትን መንገዶች ካለማቋረጥ ማሰብና መገናኛ መሳሪያዎችና ሌሎችንም ጨምሮ) በአቅም በፈቀደ መጠን ማስፋፋት። በገጠሩ የኃይል አጠቃቀም ሥርዓትን ማጎልበት። የምግብና የምግብ አዘገጃጀት ሥርአታችንን ከጤና ፕሮግራም ጋር ተስተካክሎ እንዲሄድ መላ መሻት። አዳዲስ የሚቋቋሙት የሰፋፊ እርሻ ልማት ፕሮግራሞች የሠራተኛውን ጉልበት አጠቃቀም ከግምት ውስጥ ያስገባ፤ ደህንነትና የጤና እክሎች እንዳይፈጠሩና እንዳይባባሱ ከልብ መስራት። የአዳዲስ የሠፈራና የመንደር ምሥራታ መርሃ ድርጊቶች በቅድሚያ በሕዝብ ሙሉ ፍቃድ ላይ መመስረታቸውን ማረጋገጥ። የአምራቹን ሙሉ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስጠብቁና የሚከራከሩ የተለያዩ ዓይነቶች የህብረት ሥራ ማኀበራት ማቋቋምና ማጠናከር፤ የሴት አርሶ አደሮችን ጥቅም የሚያስጠብቅ አሰራር መፍጠርና እንዲተገበሩ እገዛ ማድረግ፤ የሕዝብ ቁጥር በፍጥነት መጨመርን የሚገታ የድርጊት እንቅስቃሴዎችን ማስፋፋትና ሌሎችም በዝርዝሩ ውስጥ ያልተጠቀሱቱ በአግባቡና ከልብ ከተሰራባቸው ችግራችንን የማንቀርፍበት ምክንያት አይታየኝም።
የማንኛቸውም አገር የግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ዓይነቱ፤ ደረጃው፤ ዕድገቱና ውጤቱ በተለያዩ ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ተግባሮችና እንቅስቃሴዎች ሁሉ የተለያዩ ሊሆኑ ይችላሉ። ግብርና በዋናነት በተለይም ከማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ለየት የሚያደርገው በባህርዩ ከጸሃይ በታች በምትገኘው የተፈጥሮ ጸጋ በሆነችው በምድር ወይም በየብስ ላይ በመከናወኑ ምክንያት በርካታ አካባቢያዊና ሥነ ምህዳራዊ ተጽዕኖዎች ይፈራረቁበታል። በተጨማሪም ማኅበራዊም ሆነ ባህላዊ ተጽዕኖዎችም ለፍጥነቱም ሆነ ለውድቀቱ የማይናቁ ስፍራ አላቸው። ነገር ግን ለኢኮኖሚው መሻሻልና ለውጥ እንዲያሳይ ከተፈለገ ደግሞ ሁለት መሰረታዊ መንገዶችም እንበለው ስልቶች ወይም ሌላ በአንድነት ተጣጥመው፤ ተዋህደው፤ ተደጋግፈውና አንዱ አንዱን ተከትሎ እንዲተገበሩ ግድ ይላል። እነርሱም በዋናነት መሰረታዊና አፋጣኝ ( አቀጣጣይ / አጋዥ ሃይሎች) ተብለው ይታወቃሉ። የቀድሞው የአምቦ እርሻ ተቋም መምህሬ የሆኑትና የአሁኑ የአምቦ ዩኒቨርስቲ በረዳት ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የሚያገለግሉት በቀለ ጣሰው ናቸው ይህችን ደህና አድርገው በግብርና ኤክስቴንሺን ትምህርት ቁጥር 1 ላይ በ1971 ዓም ያስተማሩኝ። ምስጋና ለሁሉም መመህራኖቼ በዚህ አጋጣሚ።
መሰረታዊ በመባል የሚታወቁቱ የሚከተሉት ናቸው። ለግብርናው ምርት ተስማሚና በቂ የገበያ አገልግሎት መስጫ ስፍራዎች፤ ዘመናዊና በየወቅቱ እየተሻሻሉ ወደ ተግባር የሚሸጋገሩና ተመጣጣኝ የሆኑ አሠረሮች ወይም ቴክኖሎጂዎች፤ የምርት ግብዓትና የተግባር መገልገያ መሣሪያዎች አቅርቦትና በሚያስፈሉግበት ጊዜ መገኘት፤ አምራቹን የሚያበረታቱና ለበለጠ ምርትና ምርታማነት የሚያነሳሱ እርምጃዎችን ቶሎ ቶሎ መውሰድና የተለያዮ መዋቅራዊ አገልግሎቶችን ማለትም እንደ ዋናና መጋቢ መንገድ፤ ግድቦችና የመስኖ ቦዮች፤ የጎተራ አገልግሎቶች፤ ማቀናበሪያ፤ ማዘጋጃዎችና ማሸጊያዎች፤ የእንሰሳት ክሊኒኮችና የመድሃኒት ማከፋፈያዎች፤ የኃይል ምንጮችና ሌሎች በፍጥነት ማስፋፋትና ማዳረስ ዋነኞቹ ናቸው። የሚያፋጥኑ ወይም አጋዥ ሃይሎች የተባሉት ደግሞ ከዚህ ቀጥሎ የሚዘረዘሩት ናቸው። ተከታታይ ትምህርትና ሥልጠናዎች ለሁሉም በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ውስጥ በዋናነት ሆነ በአጋዥነት ለሚሰሩቱ በሞላ እንደ አስፈላጊነቱ እየተጠና፤ የብድርና የባንክ አገልግሎት በቀለጠፈና አስተማማኝ በሆነ መልኩ መቅረብ አለበት፤ አምራቾቹ የራሳችውን ዕውቀትና ክህሎት ተጠቅመው የጋራን ችግር በጋራ እንዲቀርፉ የሚያስተባብር ቡድን ወይም ማኅበር መመስረት፤ የመሬት ለምነት የሚያሻሽሉና የሚጨምሩ እርምጃዎችና ተጨማሪ መሬት ለአገልግሎት ማዘጋጀትና ከላይ የተጠቀሱትን ነጥቦች በዕቅድና በመርሃ ድርጊትና በፕሮጃክቶች መልክ መቅረጽ ናቸው።
እኔን ከሁሉ የሚገርመኝ ግን አብዛዎቻችን ተምረን ሥልጣን ላይ ቂብ ያልን ፍጡራን ሁሉ የአሁኑን ጠቅላያችንን ጨምሮ፤ የክልልና የዞን የወረዳ ባለ ሥልጣናትንም አክሎ የገዥውንም ፓርቲ አባላትን በትግራዊ ቋንቋ ለመጠቀም “ከናይ ጭቁን መደባት” እያሉ ከሚያደነቁሩን ፖለቲከኞቻችን ይዞ መነሻችንና ምንጫችን ከእዚሁ ገበሬ ቤተሰብ እንደሆን ይታወቃል። ይህም በመሆኑ የገበሬውን ኑሮ በቅርብ እርቀት የተመለከትን ይመስለኝ ነበር። በዚሁ ገበሬ ልፋት፤ ድካም፤ ጥረት፤ ጉልበት፤ ዕውቀትና ክህሎት ለአንዳንዶቻችን የተቀናጣና ለግልገሎቹ ደግሞ የተመቸ ኑሮ እንድንኖር ያደረገን ይኽው ግፉአን የተሰበሰቡበት የሕዝብ ክፍል መሆኑ ጭርሹኑ የተረሳን ይመስላል። ለእርሱ እየሰራንለት ሳይሆን እየሰራንበት ነው። እርሱ የሚያመርተውን ምርት ተገቢውን ዋጋውን ሳናጋራው እኛው አራዳውቹ በእርሱ ልፋት ሃብት በሃብት ላይ እንጨምራለን፤ በስራው ላይ ያፈሰሰውን ላቡን ሳንጠርግለት ድካሙን እንጋራዋለን፤ እንቦጠቡጠዋለን፤ እንደ ዋግምት እንመጠዋለን። እንዴት ቡናን ያመረተና ምርቱን ሁልጊዜ ገንዘብ ያላቸው እንደ ጠበል ፉት ሳይሉ ስራን መጀመር የማይሆንላቸው በዓለማችን ሞልተው ያሉ ሕዝቦች እያሉለት የአገሬ የቡና ገበሬ በባዶ እግሩ ገጀራ እየያዘ በማሳው ውስጥ ከቤተሰቡ ጋር ለትንሽ ዋጋ ይለፋል፤ ይማስናል? ልብ በሉ! ከእርሱ ምርቱን እዚህ ግባ በማይባል ዋጋ ከተረከቡት በኋላ የበለጠ ለማግኝት የሚጣደፉትን አስተውሉ፤ እንዴት ሠራተኞቻቸውን በተሻለ ኑሮ ላይ እንዳስቀመጡ። እንደምን የዓለምን “የፖለቲካ ሰብል” እየተባለ የሚጠራውን ስንዴ አምራች በድህነት ይኖራል? የስንዴ ዱቄት አምራቾቹን የማይቀመስ የፉርኖ ዱቄት ዋጋ ልብ ይበሉ! ምንጩ ይኽው መከረኛ ድሃ እየተባለ የሚጠራው ገበሬ አይደለምን? የቢራ ገብስ አምራች ገበሬን ተመልከቱና መልሳችሁ እራሳችሁን ጠይቁት? የዘይቱም ምርት፤ የዶሮውን ዋጋ፤ የከብት ስጋ ዋጋን፤ የዕንቁላል ዋጋን፤ የዓሳ ስጋን፤ የቅቤውን ዋጋ፤ የማሩን፤ የምግብ እህሉንና የጥራ ጥሬ፤ የቅመማ ቅመም ዋጋን ሌሎችንም እንደዚያው ተመልከቱት። በርግጥ ገበሬው የልፋቱና የድካሙ ተጠቃሚ ነውን ብላችሁ ታስባላችሁን? ስንቱ በዚህ ገበሬ ላብና ድካም የተሻለ ኑሮን እያጣጣመ፤ የራሱ ልጆች መልሰው ይገፉታል፤ ችግርህን አንተ አታውቅም እኛ እናውቅልሃለን ይሉታል። በቅርቡ እንኳን ግምባሩ ታንክ ይመስላል እየተባለ የሚቀለድበት በረከት ስምኦን አቅም ሳይቀር ገበሬውን እንደ ጅል ተመልክቶታል። በረከት የገበሬውን ኑሮ ከእግር ኳስ ጨዋታ ጋር ያመሳሰለው ይመስላል። የጨዋታው እንቅስቃሴ ሁሉ በዳኛው ፊሻካ ብዛትና ማነስ የሚወሰን መስሎታል። ማነው ስሙ ያ የአማራ ም/ ገዢ እንፈፍ ደግሞ በባዶ እግሩ እየሄደ ብሎ ተሳልቆበታል። ገበሬው ለልፋቱና ለድካሙ ተመጣጣኝ ዋጋ ካገኘ ለኑሮው አስፈላጊ የሆኑትን ሸቀጦች ተመልሶ መጥቶ ይገዛበታል፤ ልጆቹን ወደ ትምህርት ቤት ለመስደድ አያቅማማም፤ ጤናውን ለመጠበቅ ወደ ኋላ አይልም፤ የግብአት ብድር ካለበት ለመመለስ ወደ ኋላ አያፈገፍግም፤ በሚቀጥለው ምርት ዘመን ምን? መቼ? ስንት? ለምን? ላምርት የሚለውን መሰረታዊ የስራ ጥያቄ ጠይቆ ይዘጋጅበታል። በአገራችን ተልካሻ አሰራር ገበሬው ሁልጊዜ ተጠቃሚ ሳይሆን ተጠቂ ነው። የኔ ቢጤው ሸማቹም እንደዚያው። ተጠቃሚዎቹ የመንግስት ትልልቅ ሹመኞችና ከእነርሱ ጋር በጥቅም የተሳሰሩት ብቻ።
ለመሆኑ የግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ የሚሰጠው ጥቅም ምንድን ነው? ጠቅለል ባለ አገላለጽ እንዲህ ይጠቀሳል።
1ኛ፡ ከመሠረታዊ የሰው ልጆች ኑሮ አስፈላጊ ናቸው ተብለው በተከታታይ ከሚጠቀሱትና የክቡሩን የሰውን
ልጅ ህልውና ለመጠበቅና የምግብ ፍላጎቱን ለሟሟላት ይረዳ ዘንድ የምግብ አዝርዕቶችን ማምረት፤
ማቅረብና አዘጋጅቶ ማቅነባበር ነው። ባጭሩ የምግብ ምንጭ ነው።
2ተኛ፡ ለሌሎች ማኒፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች የሚውሉ ጥሬ ምርቶችን በማቅረብና ተጨማሪ የምርት
ውጤቶችን በማስገኘት ገደብ የሌለውን የሰው ልጆች የሸቀጥ ፍላጎት ለማሟላት።
3ተኛ፡ የኢኮኖሚ ጠቀሜታን የሚሰጡ የአዝርዕት፤ የእንስሳት ምርትና ተዋጽዎኦችን እንዲሁም ደንና ውጤቶ
ቹን ለአገርም ሆነ ለውጭ አገር ገበያ በማቅረብ የገቢ ምንጭ መሆኑና በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ላሉ
አገሮች ዋነኛ የውጭ ምንዛሪ ማስገኛና መሰብሰቢያ መሆኑ።
4ተኛ፡ ለአብዛኛው የገጠሩም ሆና የከተማ ነዋሪው ዋነኛ የስራ ምንጭ ( ጊዜያዊና ቋሚ ስራ) በመሆኑ፤ የገቢያቸ
ውን መጠን ድርሻና ዓይነት በቀጥታ ሰለሚወስን። ይቺ የሥራ ሃይል ምንጭነቷ እኛ በአገራችን
ግብርና ሲባል ከምናውቃት በላይ ነው። አብዛኛዎቻችን ግብርና ሲባል ያው ገበሬ ማረሻውን ይዞ ከአፈ
ር ጋር መታገሉና በጭቃ መለወሱና አንዳንዴም ከከብቶቹና ዶሮዎቹ ከንብ እርባታው እንቅስቃሴ ጋር
ብቻ የምናቆራኝው አለን። ነገር ግን ዕውነታው ከዚያም ባሻገር ይዘልቃል። ግብርናቸው የሜካናይዝድ
ደረጃ በደረሰባቸው አገሮች ደግሞም ሆነ በማደግ ላይ ባሉ አገሮችና የሥራቸው መሠረት ይኽው ክፍለ
ኢኮኖሚ የሆኑቱ እንደ የእርሻ መሳሪያዎችና መገልገያ ቁሶችን፤ የመሬት ማዳበሪያና የጸረ_ተባይ ኬሚካል
ማምረቻ፤ የምግብ ማቀናበሪያና ማዘጋጃ ስፍራዎቹ፤ የግብርና
ምርት ውጤቶች ማከፋፈያና መሸጭያዎች ለዓብነት ያህል የዚሁ የግብርናው የሰራ ምንጭነት ውጤት
ናቸው።
5ተኛ፡ የኅብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ የሚያስችሉ በቀጥታም ሆነ በኢቀጥታ የተዘጋጁ ፈዋሽነትን በዋናናነት የ
ሚሰጡና ለተጨማሪ አገልግሎት የሚውሉ መድሃኒቶችን ዓይነት በማምረት።
6ተኛ፡ በተለይ ከደን ልማት የምናገኘው ጥቅም በዋናነት የአካባቢን የተፈጥሮ ሚዛን በመጠበቅ፤ ለሙ አፈራች
ን በአፈር መከላት ኃይሎች ተጠርጎ እንዳያልቅና ምድረ በዳንነትን በመከላከል፤ ለብርቅዬ የዱር እንስ
ሳትም መጠለያ በመሆንና የቱሪስት መስህብ እንዲኖረው በማድረግ በዋናነት ይጠቀሳሉ። ይህንን ሁሉ ጠቀሜታውን ስገልጽም ነገ የተስተካከለና የተረጋጋ የግብርና ፖሊሲ ቢኖረንና፤ ገንዘብና ዕውቀት ኖራቸው በዚህ በምግብ ማምረት ስራ ላይ ለመሰማራት ለሚፈልጉ የአገር ሰዎች እድሉ ምን ያህል ክፍት እንደሆነና አዋጬ እንደሆነ ለመጠቆምም ጭምር ፈልጌ ነው።
በክፍል 5ትና የመጨረሻው ክፍል እስከምንገናኝ ድረስ በቸር እንሰንብት!!!
አሜን!!

ቪ ኦኤ ወይስ የኢትዮጵያ/ወያኔ ሬዲዮ ?

$
0
0

ከመስፍን ደቢ
በዚህ ባለንበት ዘመን አለማችን በሚገርም ፍጥነት ለመከታተል ፋታ በማይሰጥ ሁኔታ የፖለቲካ ለውጦች እየተካሄዱ ነው። ሶቭየት ህብረት ሲፈረካከስ ትልቁ ስባሪ ዩክሬን ነው። ዛሬ ዩክሬን እየተናጠ ነው አለምም አተኩሮበታል ። በቤንዚዌላ ቀውጢ ሆኗል ፤ አብዛኞቹ የአረብ መንግስታት ተፋጠዋል፤ በኢትዮጵያችን ደግሞ የወያኔ የመጨረሻ ምዕራፍ መድረሱ ይተነበያል። ወያኔና ደጋፊዎቹ ሽብር ላይ ናቸው። እንዲህ በምትናወጠው አለማችን የሆነውን በትክክል ማን? የት? መቼ? እንዴት? የሚለውን አንዱም ሳይቀር እንድናውቀው የሚያደርጉን ጋዜጠኞች ናቸው። ለሙያቸው ትልቅ ክብር አላቸው፣እውነተኞች ናቸው፣ ደፋር ናቸው፣ ለህሊናችው ብቻ የሚታዘዙ ናቸው፤ እውነትን ፈልገው ለኛ ሲያቀርቡና እንድናውቅ ሲያደርጉን እነሱ እስራት፣ ድብደባ፣ ስቃይ፣ ሞትም አለባቸው። እነዚህን ቁርጠኛ የእውነት አርበኛ ጋዜጠኞች እላቸዋለሁ። ስለአገራችን ብቻ ብናገር ኢትዮጵያ እንዲህ ባሉ ጋዜጠኞች ታድላለች። ተሰደውላታል፣ ታስረውላታል፣ ሞትንም ቀምሰውላታል።
ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ እና በዲያስፖራው ሁለት አይነት ጋዜጥኞች አሉ። አንዱ ክፍል የወያኔ አገልጋይ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ የሆኑ ያሉበት ነው። ሌላው ክፍል ደግሞ ለጋዜጠኝነት ሙያ ተአማኒነቱ የበረታ እውነቱን ማቅረብ ዋጋ ቢያስከፍልም ቆርጠው የሚጋተሩ ያሉበት ነው። እንዲህ ባለ አጠቃላይ ምደባ ብንጠቀም የሚቀር አንድ ክፍል አለ። የስራ ተቋማቸው በሌሎች መንግስታት የተመሰረተ ሆኖ ኢትዮጵያ ተኮር ዜና የሚያቀርቡትን ለማለት ነው። ይህም ቪኦኤ እና የጀርመን ሬዲዮ የመሳሰሉ ናቸው። በተለይ እነዚህ ተቋማት ቪኦኤ የአሜሪካን ጀርመን ሬዲዮ የጀርመን ናቸው። ኢትዮጵያ ተኮር ዜና በአማርኛ፣ በትግርኛ፣ በኦሮምኛ፣ በሱማሊኛ ያቀርባሉ። ኢትዮጵያውያን በአገር ውስጥ እና በውጭ እንደ አማራጭ የዜና ምንጭ ይጠቀሙባቸዋል። በእነዚህ የዜና አውታሮች ያሉ ጋዜጠኞች የአሜሪካን ወይም የጀርመን መንግስትን አቋም እንዲያንጸባርቁ ቢገደዱ እንረዳቸዋለን ከዚህ በተረፈ ግን ለተግባራቸው መሪ ህሊናቸው ብቻ ነው ብለን እናምናለን። ለእውነት መቆምን፣ ሚዛናዊ መሆንን ያለውን እንዳለ የሆነውን ያለተጨማሪ አስተያየት ለአድማጩ ማቅረብ ሙያው የግድ ይላል ፡የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ጋዜጠኛ የኢትዮጵያ ሬዲዮ የለቀቀውን ውሸት ቢያስተጋባው የምንታዘበው ይሆናል። ቪኦኤ የኢትዮጵያ መንግስታዊ የዜና ተቋም ያለውን ቢያስተጋባ ትዝብት ላይ ይጥለዋል:: ቪኦኤ በዲያስፖራው ካሉ የወያኔ “የዜና” የፕሮፓጋንዳ ጋዜጠኞች መለየት አለበት ። ቅዳሜና እሁድ በመጣ ቁጥር አምባሳደር ኢንተርቪው የሚያደርጉና ስለልማት የሚያወሩ ባዶ ገረወይና የሆኑ አሉ። ቪኦኤ ከነዚህ መለየት አለበት።

ቪኦኤ በሞያቸው የተከበሩ ጋዜጠኞች ያሉበት ተቋም ቢሆንም ደግሞ ደጋግሞ ስህተት የሚፈጽም ረቀቅ ባለ መንገድ የወያኔን አቋምና መልእክት የሚያቀርብ ጋዜጠኛም አለበት። ይህ መሆኑ ደግሞ ያሳዝናል ። ለምሳሌ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይሮፕላንን አቅጣጫ አስቀይሮ ጄኔቭ እንዲያርፍ አድርጎ የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቀው ረዳት አብራሪ ሀይለመድህን አበራ ድርጊቱ በአለም የዜና አውታሮች ሁሉ ቀርቧል። ከሁሉም የዜና አውታሮች ግን ቪኦኤ እና የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቲቪ የዘገቧቸው ይመሳሰላሉ። ሁለቱም ያተኮሩት የሀይለመድህን የአእምሮ ሁኔታ ላይ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት ስለ ሀይለመድህን አእምሮ ማተኮር የፖለቲካ ብሶቱና በደሉ እንዳይሰማ እና እንዳይተኮርበት ለማድረግ ነው። የቪኦኤውም “ጋዜጠኛ ” ይህን የማድረግ ግዴታ የለበትም ሚዛናዊ በሆነ መልኩ መዘገብ በቻለ ነበር። በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲህ ያለ የተዋጣለት ወጣት ሙያተኛ ምን ምክንያቶች ላደረገው ድርጊት ጋፋፉት ብሎ ጥያቄውን ወርውሮ ማለፍ ይችል ነበር፤ ግን መልእክቱን ጋዜጠኛው ከኢትዮጵያ ሬዲዮ ጋር በረድፉ ለማሰለፍ የቆረጠ ስለሚመስል የአእምሮ ሁኔታ ላይ አተኮረ፤ ሁኔታውም ካለማወቅ አይመስልም።
ዛሬ ዘመናችን አማራጭ የዜና ተቋማትን ቴክኖሎጂ ያንበሸበሸን ዘመን ነው። እንደ ዱሮው ቪኦኤ ወይም የጀርመን ሬዲዮ ብቸኞቹ የነበሩበት ግዜ አይደለም። የኢትዮጵያ ህዝብ በሀገር ቤትና በውጭው ይህን እውነታ ያውቃል። ቪኦኤ ለራስህ ብለህ ጣፍጥ ነው መልእክቱ ። ልጅ ያቦካው ለራት አይበቃም እንዲሉ ምራቃቸውን ዋጥ ያደረጉትን ጥቅም ሊያማልላቸው የማይችሉትን የእውነት አርበኛ የሆኑትን ጋዜጠኞች ከፊት ረድፍ ቢያሰልፉ ለቪኦኤ ጠቀሜታ ይኖረዋል። ቀድሞ እንደተባለው ኢትዮጵያ የጀግኖች እና የእውነተኛ ጋዜጠኞች ባለ ጸጋ ነች፤ ገና ብዙ ታፈራለች።ብዙ ጀግና ጋዜጠኛ የሚወለድበት የለውጥ ማእበል እያስገመገመ ነው። መጥኔ ለቪኦኤ እራሱን ካላረመ፤ ሰሚ ያጣ ጋዜጠኛ ከመሆን ሰውረኝ ነው።
ቪኦኤ አንዱ ጋዜጠኛው አግባብ የሌለውን ተግባር ቢፈጽም እንደ ተቋም መጠየቁ አይቀርም። ሄኖክ ሰማእግዜር ባደረገው ነገር ትዝብት ብቻ ሳይሆን በጣም አዝነናል ቆይቶ ደግሞ ህዝባዊ ቁጣ ማስነሳቱ አይቀሬ ነው።

አሜሪካ የበለጠ ትናገር! (ከጸጋዬ ገብረመድህን አርአያ)

$
0
0

“ ነፃነቴን ካልሰጣችሁኝ ሞትን እመርጣለሁ”
ፓትሪክ ሔንሪ Give me Liberty or Give me Death

ፍሬደሪክ ዳግላስ (1818- 1895) ከባርያ እናትና ከነጭ አባት የተወለደና ራሱም ቢሆን በቦልቲሞር (ሜሪላንድ) የቤት አሽከር ሆኖ የቆየ ሰው ነበር። አንድ ማለዳ ጁላይ 4 ቀን 1852 ን ተንተርሶ (አንተርሶ) በሮቼስተር ከተማ (ኒውዮርክ) ንግግር እንዲያደርግ ጥሪ ይደርሰዋል። ደብዳቤው ሲደርሰው እንደ እብድ ከራሱ ጋር መነጋገር ያዘ። መቸም አንዳንድ ጊዜ እንዲህ ያለ ለማመን የሚከብድ አጋጣሚ ሲመጣብህ ናላህ ይበጠበጣል። ፍሬደሪክ ዳግላስም “በእርግጥ ይህ ደብዳቤ ለእኔ የተጻፈ ነው? የተቀባይ ስምና አድራሻ ስሕተት ተፈጽሞ ይሆን?” ሳይል አልቀረም። ዳግላስ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ጭንቅላቱን ሲበጠብጥ ቆይቶ ትንሽ አረፍ አለ። ሲነቃ ይኸ ዕድል እንዳያመልጠው ፈለገ። ይልቁንም የሚናገርበት ርዕስ መጣለት። “ በመሰረቱ እኔን ባርያውን በዚህ በዓል ላይ እንድገኝ- ለዚያውም ተናጋሪ መሆኔን ሳስበው ይህ ሁሉ ግብዝ- የግብዝም ግብዝ ነው አለ። ይበልጥ ደግሞ ለተሰብሳቢው ስለጁላይ 4 (ነፃነት በዓል) እንድናገር እኔን ባርያውን መጋበዛቸው ሌላው ግብዝና ነው ” አለ። ለማንኛውም ንግግሩን አዘጋጀ። በዚያ ወቅት በሮቼስተር ከተማ ያደረገው ንግግር እስከ ዛሬ ድረስ ከዓለም ታላላቅ ዲስኩሮች አንዱ ለመሆን በቅቶአል። “ጁላይ 4 ቀን ለመሆኑ ለባርያው ምኑነው? What to the Slave is the Fourth of July?

ዛሬ ከብረት በከበደ ክንድ ኢትዮጵያን እየገዙአት የሚገኙት ጌቶች- አዳዲስ መሳፍንት- አዳዲስ መኳንንት፣ አዳዲስ ዲታዎች…የንግስ በዓል ከሳምንታት በኋላ ይከበራል። (በዩጐዝላቩ ጂላስ The New Class, ወይም ከሮማውያን ዘመን አንስቶ Nouveau Riche ቀላል ድግስ አያውቁም። ስለዚህ ጉንበት 20 ቀን በታላቅና ታይቶ በማያውቅ ድምቀት ይከበር ዘንድ ዝግጅቱ እየተሟሟቀ ነው። አገር ያፈራው ትልልቁ የሐረር ሰንጋ፣ ወደል ወደል የሚያክለው የወለጋ ላታም በግ ወዘተ ተመርጦ ተመርጦ ይቀርባል። ሻምፓኙ፣ ውድ ውዱ አይሪሽ መጠጥ- ዊስኪ፣ ድራንቡዬ፣…የፈረንሳይ ኮኛኮች፣ ምርጥ ወይን ጠጆች..ያልፍላቸዋል። ምንም ማጋነን የለበትም። ጫካ ውስጥ በነበሩበት ጊዜ እንኳ ለድግስ ስንትናስንት ሚሊዮን ብር ሲያወጡ እንደነበረ ከጉያቸው የወጣው ጠንካራ ኢትዮጵያዊ…ገብረ መድኅን አርአያ ገልጦታል።
“ኑና ጉንበት 20ን አብረን እናክብር” ተብለው የተጠሩ ወይም እንጠራለን ብለው ቀኑን እንደወላድ እየቆጠሩ- የራቀባቸው ሰዎች የሉም አትሉም። እናንተም እንደኔ። ከውጭ የሚጋበዙ በርካታ ሰዎች ይኖራሉ። አዳራሾች-ሆቴሎች- በየደረጃው… ላይበቁ ነው። እሸሸ ገዳሜው፣ አስረሽ ምቺው ደግሞ የሚጠበቅ ነው። ስለገዢዎቻችን ሀብትና ንብረት ያልተባለ ነገር የለም። ይኸ ደግሞ የሞራሉን ቁልቁለት ምንኛ እንደ ተያያዙት ስም እየጠቀሰ መረጃ የሚሰጠንን ውስጥ አወቅ ኢየሩሳሌም አርአያን ማድነቅ እወድዳለሁ። በሽምግልናና ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ በሚገባቸው ዕድሜ የእኝኝ ብላ ባዝራዎች፣ አንድና ሁለት (በቀን) የማይበቃቸው የወንድ መለኮኖች አሉባቸው። ከዚህ ተራ ውስጥ ሁለት ሰዎችን ብቻ (በረከተ-መርገም ስምዖንና ስዬ አብርሃ) ነፃ ያወጣቸው ደግሞ ተስፋዬ ገብረ-አብ ነው። ስለሆነም ዳንኪራውና ስድ የሆነው በዓል የሚጠበቅ ነው። እኛም የኢትዮጵያ ጉስቁሎች የሌላ ሕዝብ በዓል በሥነ ሥርዓት መጠበቅ አለብን። የበዓሉን መንፈስ ማደፍረስ፣ ማደናቀፍና ማቃወስ በአሸባሪነትና በመሳሰለው አንቀጽ ያስቀጣል። አዎን ጉንበት 20 ቀን የድግሦች ድግሥ፣ አውራ በዓልና የድግሦችና የበዓሎች ሁሉ እናት ናት። ማን ያውቃል? ድሮ ጃንሆይ አጤ ኀይለ ሥላሴ ሐምሌ 16ን “የትዮጵያ የልደት ቀን” እንዳሉአት እነዚህ አዳዳሶቹ መሳፍንትም ጉንበት 20ን “እውነተኛው የኢትዮጵያ ናጽናት ቀን” ቢሉት አይደንቀኝም። ( ብቻ ማን ነበር- የአንዱ ሕይወት የሌላው መርዞ ነው- ያለው?)
በአገራችን የድግስ ነገር ሲነሳ ትንሽ የማስታውሳቸው ነገሮች አሉ። በአጤው ጊዜ ጃንሆይ የተወለዱበት (ሐምሌ16) እንዲሁም የነገሱበት (ጥቅምት 23) ይከበሩ ነበር። ለኢትዮጵያ ባሕልና ፖለቲካ እንግዶች የሆናችሁ ወጣቶች ምናልባት አታውቁት ይሆናል እንጂ በክብርም ቢሆን ቤተ መንግስት ስትጠሩ ግርግሩ ብዙ ስለሆነ ትንሽ ጨፈቃ ትቀምሳላችሁ። እንጀራው በእግር የተቦካ ነው ይባላል። ለማንኛውም “የንጉስ በረከት” አይናቅም ትባላላችሁ። (ይህንን የበለጠ ለማወቅ ፍቅር እስከ መቃብርን ያነብቡአል) ወደኋላ ጊዜ የሐምሌ 16 በዓል አከባበር ለአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ተሰጥቶ ነበር።
የድግስ ነገር- በመንግስት ሰፈር- ብዙ ምልኪ አለበት። ስለ ጃንሆይ መንግስት አወዳደቅ ብዙ ቢባልም ለጊዜው አንዱን አነሳለሁ። አንዳንድ ሚኒስትሮች እጅግ ከቅብጠትም ባሻገር ስለሄዱ ክራር ይዘው ወደ መሸታ ቤት መሄድ አብዝተው ነበር። የዛሬዎቹ ከእነዚያ ጋር ባይወዳደሩም ትንሽ ትንሽ ሕዝብንና አኗኗሩን ወደ መርሳቱ ደርሰው ነበርና ሌላው ቀርቶ ከመሳፍንቱ አንዱ የነበሩት ጄኔራል ዐቢይ- “አውቀን እንታረም” የሚል መጽሐፍ ደርሰው ነበር። ጠንቃቃው ጄኔራል “አውቀን ካልታረምን ሌላው ቀርቶ ሬሳችን እንኳ የወደቀበት አይታወቅም” ብለው ነበር። አዎን አርማጌዶን በዓለም ፍጻሜ ላይ የሚከሰት ሳይሆን ያልታሰበ የእልቂት መውረድም አርማጌዶን ሊባል ይችላል። ያ ወቅት የሞራል ድቀት ሥጋና ደም ገዝቶ የሚታይበት፣ ሕዝብ ሲያልቅ አንዳንድ ሹማምንት መንደላቀቅ ያበዙበት ነበር። ደርግ ጃንሆይን ከሥልጣን ሲያወርድ “ሕዝብ በሺህ ቤት ሲረግፍ እነሱ በእሸሸ ገዳሜ ተጠምደው…” እያለና የቀለጠ ድግስ በቴሌቪዥን እያቀረበ ነበር። ድግስ….
ደርግ ራስዋ በራስዋ ያመጣችው ጣጣም አለ። ወደ ሥልጣን የመጣበትን ቀን ለማክበር ብልጭልጩንም ማናምኑንም ሰልፉንም…ሲያበዛ የእንግሊዝ ጋዜጠኞች በሁለት መቶ ሺህ ዶላር ውስኪ ሸጥን አሉና…የደርግ መሰላል ወደታች ብቻ የሚያወርድ ሆነ። ድግስ እየተኮነነ መጣ። ድግስ እየተጠቀሰበት ወረደ። ሁለት መቶ ሺህ ሕዝብ በረሃብ አለቀ ብሎ ተሳለቀ ተባለ። በራሱ ጊዜ ዘጠኝ ሚሊዮን ሕዝብ ተርቦ ውስኪ ተራጩ ተብሎ ለወያኔ ፕሮፖጋንዳ ተመቸ። እዚህ ላይ ያነሳሁት የጉንበት 20 አከባበር ያንኑ እድል ይከተል ይሆናል- ይከተላልም- ቁልቁለቱን ጀምሮአል በሚል ነው። ድግሶች በሦስቱ መንግስታት- የሥልጣን መልቀቂያ ጊዜ ምልክቶች- ብልሽትሽቱ የወጣ መንግስት ማክተሚያ ወቅቶች ሆነው አይተናቸዋል። ( ሁሉም የእጁን ያገኛል- ብድሩን ወይም ብድራቱን ተከፈለ- በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀርም የሚባል አነጋገር ያለ ይመስለኛል። የእንግሊዝኛው ፈሊጥ ግን Poetic Justice ይለዋል) “ያርግላቸው!” አሜን ያድርግላቸው!!
ደርግ የተወነጀለበት 200ሺህ ዶላር ዛሬ አንድ ባለ ጊዜ ወያኔ ለልጁ ልደት ከሚደግሰው በታች ነው። በ1997ዓ.ም አባዱላ ገመዳ ለልጃቸው ዘኪያስ አባዱላ 24ኛ ልደት በዓል የ100ሺህ ዶላር ኮብራ ዘመናዊ መኪና በስጦታ መልክ አበርክተዋል። በ1994ዓ.ም በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ 14ሚሊዮን ሕዝብ ለረሃብ ተጋልጦ ነበር። መለስ ዜናዊ ከ10 ዓመት በኋላ “በቀን ሶስት ጊዜ ትበላላችሁ” ባሉበት ዓመት መሆኑ ነው። የመለስ ዜናዊ መንግሥት ለተራቡት ወገኖች ደንታ አልነበራቸውም። በድርጅታቸው የተፈጠረው ቀውስ ላይ በማተኮርና ለእርሳቸው የሥልጣን ዕድሜ ማራዘሚያ ሲሉ “ተሃድሶ” ብለው ለሰየሙት ቱማታ 280ሚሊዮን ብር ባጀት መድበው ካድሬዎቻቸውንና ተከታዮቻቸውን በድግስና በውስኪ ያምነሸንሹ ነበር። በዛው ዓመት ልጃቸው ሠማሃል መለስ የልደት በዓልዋን በግዮን ሆቴል ዳስ ተጥሎ አክብራለች። ለኬክ ብቻ ግማሽ ሚሊዮን ብር ነበር ወጪ የተደረገው። የመለስ ልጅ ልደትዋን በምታከብር እለት በግዮን ሆቴል ደጃፍ በርካታ በረሃብ የገረጡ ወገኖች የሚላስ የሚቀመስ አጥተው ወድቀው ነበር።
ስለ ድግስ ዝርዝር ለመጻፍ ፍላጐቱ የለኝም። ደግሼም አላውቅም። መንግስት ሲቀናጣ፣ እሸሸ ገዳሜው ልክ ሲያጣ፣ የሞራል ድጡ መጠነ ቢስ ሲሆን፣ ሰብአትካትን- ሰዶምና ገሞራን ወይም የጥፋት ውሃን ዘመን ሊያመለክተን ይችላል። ራስ ተፈሪዎች “ባቢሎን” ይሉታል። እንዲያውም በቀድሞው መንግስት በጠቅላይ ሚኒስቴር ሚኒስትር የነበሩት ዶክተር ሥዩም ሐረጐት The Bureaucratic Empire, Serving Emperor Haile Selassie በሚለው መጽሐፋቸው ያነሱት አንድ ነጥብ ስለድግስና ስለመሳሰሉት ጉዳዮች ነበር። ኮረኮረኝ። ሥዩም ሐረጐት እንደጻፉት የቀ.ኀ.ሥላሴ ባለስልጣኖች የታሰሩት ጠጅ ለመጣል ምቹ ቅዝቃዜ በነበረው ሥፍራ ነበር። ከላይ የደርግ አባላት ስብሰባ ሲካሄድ፤ ሑካታ ሲፈጠር፣ ጭብጨባ ሲበዛ ወዘተ በእሥረኞቹ ላይ ይፈጠር የነበረውን የመንፈስ ጭንቀት ይነግሩናል። አሳሪዎች የእሥረኞች ሥቃይ ሊታያቸው ከቻለ በእርግጥ “ሰው” የመባል ሙሉ ባሕርይ አላቸው ለማለት ይቻላል። (የደርጉን ዘመን ግፍ ለማውራት የምደፍርበት ወኔ የለኝም። ራሳቸውን እየቀደሱ በሌሎች ግለሰቦች ላይ ከሚደነፋፉም ጋር ጠበል የምጠጣ አይደለሁም። አንድ ነገር ላይ ከተስማማችሁልኝ ደርግ በውሃ አጥምቆ ቢሆን ወያኔ ይኸውና በእሳት እያጠመቀ ይገኛል። የጥምቀቱ ተቀባይ ደግሞ መላው ወገኔ ነው።)
የአሜሪካ መንግሥት ባለፉት ቀናት የኢትዮጵያን ድንኳን ገለጥለጥ አድርጐ የአገሪቱን የሰብአዊ መብት አጠባበቅ፣ የፖለቲካ እሥረኞች አያያዝ፣ በገጠር ያለውን ብሔረሰቦችን የመከፋፈል መንግስታዊ ጫናና ወንጀል አሳውቆናል። አሳውቆልናልም። በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ሰማንያ ሺህ የፖለቲካ እሥረኞች አሉ። ከእነዚህም መካከል ስድሳ ከመቶው አእምሮ እስከ መሳት መድረሳቸውን በምስክርነት አቅርቦልናል። ዝርዝሩ ብዙ ነው። ታላቅ ወንድም (የተጠጋኸው ትልቅ መንግሥት በፖለቲካው ቋንቋ ቢግ ብራዘር ይባላልና) ምናልባትም የእሥረኛውን ቁጥር ቀንሶት ይሆናል እንጂ በኢትዮጵያ እየኖረ ወያኔንና ትውልደ ወያኔ ያልሆነ ለመሆኑ ያልታሰረ – አለዚያም እሥራት የማያስጨንቀው ማነው? ብለው የሚጠይቁ የትየለሌ ናቸው። ያልታሰሩ የሚመስላቸው ሰዎች ደግሞ የጥርስ ችግር እያለው ሕመም ሳይሰማው በመጨረሻ ላይ አምስትና ስድስት ጥርሶቹ ሲረግፉለት ለቃቅሞ ወደ ሐኪም ቤት እንደሚሮጥ ሰው ናቸው።
እንደሁም ልጆቻቸው ወይም የአገር ወጣቶች በነቂስ እየታረዱ ኅዘኑ ከቤታቸው የማይገባ፣ የቤተሰብ አውራ በባለቤቱ ፊት ታስሮ ሚስት ስትነወር፣ ንብረቱ ሲድፋፋ፣ ጐታው ሲደፋ ልቅሶውና ዋይታው ከጆሮአቸው የማይደርስ ጐረቤት ወገናችን አለ። የድንጋይ ልብ የገባለት። አንዳንድ የማውቃቸው ሰዎች – ጐይትኦም ብቻ ሳይሆን- ደባልቄና አምበርብርም ጭምር – ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ ሄደው ሲመለሱ ተመሣሣይ ትዝታ ይዘው ይመጡላቸዋል። አዲስ አበባ ውስጥ የሚሠራው የእድገት ምልክት የሚገለጥ አይደለም። የአለቃ ደስታና የተሰማ ግጽው መዝገበ ቃላት በቂ ቃላት የላቸውም። “እንዲያውም በእንግሊዙ ንገረኝ” ትለዋለህ። አንተም አሿፊ እሱም አሹዋፊ ትባላላችሁ። ጓድ መንግሥቱ ኅይለማርያምን ብጠቅስ እንደማትቀየሙኝ ተስፋ አደርጋለሁ። በኢትዮጵያ ራዲዮ በሠራሁባቸው ዓመታት አንድ ቀን ስለ ራዲዮ አሠራር ስንገልጽላቸው ምርር ትክን ብለው “ ዘፈኑና ጭፈራው አልበዛም ወይ? ለመሆኑ ወገኖቻችን በጠላቶቻችን ሰይፍ እየተመቱ፣ አብዮታዊ ሠራዊታችን በግራም በቀኝም – በሰሜንም በምሥራቅም፣ በመሐል አገር ደግሞ በአምስተኛ ረድፈኞች ጓዶቻችን ሁሉ እተየረሸኑ..እያለቅን አይደለም ወይ? ኢትዮጵያ ራስዋ እንደ አንድ ልቅሶ ቤት መታየት የለባትም ወይ? እንዴት ነው በዚህ ሁሉ ልቅሶኛ ላይ እሸሸ ገዳሜ ዘፈን ለማሰማት ፈቃድ የምትፈልጉት? ፈቃድ የሚጠየቅበት አይደለም። እንደየስሜታችሁ ነው። ደስ ካላችሁ ዝፈኑ። አስዘፍኑ። አለዚያም ዳኝነቱ የእናንተ ነው” ብለው ነበር። አንዱ ሲደሰት ሌላው ያዝናል። ዓለም ጉራማይሌ!
ሕይወት ከዚህ መሠረታዊ አመለካከት ይጀምራል። ግን ከአለቃችን ንግግር ውስጥ ማንንም ሊነካ የሚገባው ለአገራቸው ባበረከቱት ቅንና ሕጋዊ አገልግሎት ምክንያት እንደ ወንጀለኛ ተቆጥረው ወደ ወህኒ ዓለም የተወረወሩትን ሰማንያ ሺህ ኢትዮጵያውያን በዓይነ ሕሊናችሁ ጐብኙልን። አሜሪካ የምትነግረን- የማናውቅወን አይመስለኝም። ራስዋን በምስክርነት አቅርባለች። ከተጠቀምንበት። ወይም ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ አንድ ሰሞን ይሉ እንደነበረው “በደርግ ጊዜ አሜሪካ በክምር ሳር ውስጥ የወደቀች መርፌ ይታያት ነበር። አሁን ግን በእልፍኝ ውስጥ የቆመው ዝሆን እንዳይታያቸው አንድ ዓይነት ግርዶሽ (ማዮፕያ) ተፈጥሮባቸዋል” አይደለም? ጉዳዩ የኢትዮጵያውን ጉዳይ ነው ተባብለናል። የኢትዮጵያን ዋና ዋና ትግሎች (ጦርነቶች) በቅጥረኛና ካልሆነም በአሜሪካ አማካይነት የምንዋጋቸው አይደሉም። ይልቁንም ዛሬ አሜሪካ የነገረችን ሁላችንም እሥረኝነት እንዲሰማን ይመስላል። ጐበዞቻችን በወህኒ እየማቀቁ ነው።
ስለ እስክንድር፣ ስለ በቀለ፣ ስለ አንዱዓለም፣ ስለ ርእዮት….ሰምተን ነበር? ከእነሱ ሌላ ሰማንያ ሺህ ማን ያውቃል 180ሺህ ሰዎች በወህኒ ዓለም ይማቅቃሉ። ሌሎች ያልታሰሩ ግን “በመተካካት መልክ” ሊገቡ ወረፋ እየጠበቁ ናቸው። አፍጥጦ የመጣብን- እስካሁንም ያልተመለሰው ከባድ ጥያቄ- ለመሆኑ እኛስ አልሞትንም ወይ? መቸም ወደፊት እንደምንተሳሰበው ከሞቱት አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ አምሳ ሺህ ውስጥ አይደለንም ወይ? የመኖር ያለመኖር ማረጋገጫ (ምናልባት ሰርተፊኬት ወይም ሊቸንሳ) አግኝተናልን? ራስ ቢተወደድ መኮንን እንዳልካቸው “አልሞትሁም ብዬ አልዋሽም” ነበር ያሉት? ሙኩሼዬ ጸጋዬ ገብረ መድኅን ቀዌሳ ደግሞ ልዑል ሐምሌት የሚያንበለብለውን ዘላለማዊ ስንኝ እንዲህ ብሎ በከፊል ወደ አማርኛ መልሶታል።
መኖር አለመኖር እዚህ ላይ ነው ምሥጢሩ
የዕድል ፈተና አለንጋ ሲወናጨፍ ወስፈንጥሩ
ይህ ዕድል ያልደረሰውና የፈተናውም አለንጋ ያልገረፈው አለ ወይ? ይለናል። ኦስካር ዋይልድ ይመስለኛል በሶሻሊዝም ሥር የሰው ነፍስ (The Soul of Man under Socialism) ድርሰቱ “መኖር እጅግ ብርቅ ከሆኑ ባሕርያት ዋነኛው ነው። ብዙ ሰዎች እንዲሁ አሉ። ግን አይኖሩም ” ያለው (To live is the rarest thing in the World. Most people exit, that is all ) ይለናል በአንክሮ። የእኔው የትግል አድባር (አያውቀኝም) ፕሮፌሰር ሐጐስ ገብረ ኢየሱስ እናቱን ለመጠየቅ ጓድ መንግሥቱ ሔሊኮፕተር አዘዙለትና ወደ አድዋ ሔዶ ነበር። ሲመለስ A Requiem of History በሚል ያቀረበውን መጣጥፍ አልረሳውም። በዚያው ሰፊ ጽሑፉ ውስጥ እንደ ፈርጥ ያየሁለት “እናቴ በእርግጥ በሕይወት አለች። እየኖረች ግን አይደለም። She was alive, but Not living.” ይላል።
በ1980ዎቹ ካነበብኋቸው መጻሕፍት መካከል በሔንሪ ኪየምባና በዴቪድ ማርቲን የተገለጡ አስደንጋጭ አጋጣሚዎች በአእምሮዬ ውስጥ የተከሉት ክፉ ትዝታ አለ። በኢዲአሚን ኡጋንዳ ጊዜ የተፈጸመ ነው። እንዲያውም የ“State of Blood” የሚለው ጸሐፊ የኡጋንዳ የጤና ጥበቃ ሚኒስተር የነበረው ሔንሪ ኪየምባ ነው። ወደ ወጉ እንመለስና ኢዲአሚን በየቀኑ ሥፍር ቁጥር የሌለው ኡጋንዳዊ የሚገድልበትና የጭፍጨፋው ወፍጮ እንበለ እረፍት የሚሠራበት ሥፍራ ነበር። በዚህ “ሥራ” ላይ የተሰማሩት ባለሙያ ነፍሰ- ገዳዮች ትንሽ ፋታ ካገኙ ወደ ሰፈር መሸታ ቤት ይሄዱና ካቲካላና ቡቅር ከሚመስለው “ነፍስን ጭምር” ከሚያስረሳው መጠጥ ይጨልጣሉ። ግድያው እንደ ጫት ሐራራ ስለሆነባቸው በማይገድሉበት ሰዓት ሁሉ ሲያፋሽጉ ይውላሉ።
አንድ ቀን ያለወትሮው ግድያው በምሽት ሰዓት ሊጠናቀቅ ስላልቻለ ዋናው ገዳይ እስረኞቹን ይሰበስብና “ዛሬ ስለመሸ ሄዳችሁ ከቤተሰቦቻችሁ ጋር እደሩና ነገ በጠዋት መጥታችሁ መቃብራችሁን ቆፍራችሁ ትገደላላችሁ። አሁን ሂዱ። መልካም ዕድል” ይላቸዋል። በማግስቱ እስረኞቹ ተሽቀዳድመው በመሰለፍ መቃብራቸውን ቆፍረው በተሰጣቸው ትልልቅ መዶሻ አንዱ ሌላውን ገደለ ይባላል። ተረት ወይም የፈጠራ ድርሳን አይደለም። ዴቪድ ማርቲን በኦብዘርቨር ጋዜጣ ላይ በተከታታይ ያቀርብ የነበረውን ሐተታና ከላይ በርእሱ ያመለከትሁትን የሔንሪ ኪየምባ መጽሐፍ ያነብቡአል።
ገዥዎቻች፣ አንዱን ጠባብ፣ ሌላውን ነፍጠኛ በማለት የሰየፉት ወገን ቁጥር ይታወቃል? ከምዕራብ ወደ ደቡብ፣ ከደቡብ ወደ ምዕራብ እያንከራተቱ በየኪሎ ሜትሩ የረገፈው ወገናችን ቁጥር ይታወቃል? በአኅዝ የማይገለጠው መከራውና ሰቆቃው በምን ይተመን? እዚህስ ደረጃ አልደረስንም የሚያሰኝ ምን ምልክት አለ? አሁንም ለእርድ የተዘጋጀን ነን- ሁላችንም ባንሆን አብዛኞቻችን። ንጹሐን ዜጐችን ግደሉ ብንባል ዓይናችንን የማንጨፍን አለን። አሁንም ቢሆን እኛን በእኛ እየጨረሱንም እያጫረሱንም ነው። አይደለምን? የኢዲአሚኑ ሪፖርት ይዘገንናልን?
ያንን የምታውቁትን ለፍቶ ያስተማረኝ የኢትዮጵያ ገበሬ ሲባልለት የቆየውን “ናስቲለው”…አልፎ አልፎ ታስታውሱታላችሁ? ትዝ ሲላችሁ ዓይናችሁ እንባ ይቋጥር ይሆን? (ናስቲለው በሰሜን ኢትዮጵያ ገበሬ ማለት ነው።) አሜሪካ ስለ ኢትዮጵያ ገበሬ በመንግስት መሰቃየት ያርዳን? አቦ! አቦ! እንደ ብዕርና ወረቀት ያስጠላኝ ነገር የለም። ካሣ ተሰማ ትዝ አለኝ። ድንቀኛው ጸሐፊ ጓደኛዬ ብርሃኑ ዘሪሁን ካሣ ተሰማን አንድ ቀን አነጋግሮት ነበር። ለመነን መጽሔት ነበር። ብርሃኑ ወርቅ የሆነውን የካሣን ፕሮፋይል ሲያቀርበው “ቧንቧ ሠራተኛው ካሣ” በማለት ነበር። ካሣ ክራር መደርደር የለመደው በስሜት ነው። ከተቃጠለ አንጀቱ የሚያወጣውን ትንፋሽ በዘፈን ለማብረድ ነው። ካሣ ይዘፍናል። ስሜቱ ወደ ጽርሐ-አርያል ይከንፋል። እሱም ራሱ እንደ ማኰብኰብ ሲለው ክራሩን ሰባብሮ ሲጃራ መግዣ ፍለጋ ይሄዳል።
ይኸ ሁኔታ ዛሬ ይገባኝ ጀምሮአል። ከክራሩ ባሻገር የሚሰማው ድምፅ ያለ ይመስለኛል። ከመላእክት ጋር ሲነጋገር ቆይቶስ ቢሆን? ከአድማስ ባሻገር ከታላላቆቹ ተራሮች ላይ ሆኖ ስለዚች አገር ዕድል- ስለሚደርስባት አደጋ፣ ስለ ትንንሽ ልጆችዋ መቀጨት፣ እንደ ዛሬ ስላለው የመከራ ሌሊት ያጫወቱት እንደሆነ ማን ያውቃል? እንዲያ ሆኖ ሆኖ ካሣ ወደ ቧንቧ ሥራው ይመለሳል። እሱም ዘመንን ቆጥሮ ወደ መሬቲቱ ተመለሰ። ወደ ማኅፀናዋ።
እኛንም ደካሞች ልጆችዋንም እነሱንም ባሊጊዜና ቅምጥል አዳዲስ መኳንንትና መሳፍንት የኢትዮጵያ መሬት እኩል ትበላናለች ወይ? ስለ ጄኔራል ደጐል ያነበብሁት አንድ ታሪክ አለ። ጄኔራል ደጐል ሽባ ሆና የተወለደች ልጅ ነበረቻቸው። ወላጆች እጅግ እያዘኑ ልጅቱ በመንፈስ እንድትጠነክር የማያደርጉት አልነበረም። የሚችሉትን ጥረት ሁሉ ካሙዋጠጡ በኋላ ልጅቱ ትሞታለች። እናት መሆን አይቀርምና ማዳም ደጐል ምርር ብለው ያለቅሳሉ። ያዝናሉ። እሳቸውን ማጽናናትም ከባድ ሆነ። በዚህ ጊዜ ጄኔራል ደጐል ባለቤታቸውን “እስካሁን ድረስ ምኞታችንና ጸሎታችን ሁሉ እግዚአብሔር ከሰው እኩል እንዲያደርጋት ነበር። ይኸውና በሕይወት ባይሆን በሞት ከሁሉ ጋር እኩል ሆናለችና ልቅሶሽን ተይ…” በማለት ባለቤታቸውን አጽናኑአቸው።
ኢትዮጵያውያን ሽባ ሆነን አልተፈጠርንም። ወይም አዳዲሶቹ ዲታዎች (ኖቮሪሽ) በአፋቸው ላይ የወርቅ ፍልቃቂ እየነከሱ ከማኅፀን አልወጡም። ሕዝብ የሚገዛው እንዲህ ነው ተብለው ጊንጥ የሚመስል አለንጋ የሰጣቸው አንዳች ኅይል የለም። ለምን ገዥና ተገዥ፣ ገራፊና ተገራፊ ሆነን ቀረን? አንመራመር። አስፈላጊ ወዳልሆነ እሽኰለሌም አንግባ። ይልቁን ከሞት በፊት ስላለው እኩልነት እናንሳ። በሞት ሕይወትን ስለማምጣት፣ በደምና በአጥንት ነፃነትንና እኩልነትን ስለመቀዳጀት።- ውይይይይ ለአፍ አይገድም። ትግሉን፣ መስዋዕትነቱን በወረቀት ላይ ጨረስነው አይደል? በሃያኛው ክፍለ ዘመን መነሻ የተጫነው የእኩልነት ትግል እነ W.E.B Du Bois የጀመሩት የጥቁር አሜሪካውያን ተጋድሎ ስትራተጂ የሚነደፍበትና ፕሮግራሙ በሥራ ላይ የሚውልበት ስልት የሚወጣበት ነበር። ታላቁ ዱብዋ ተፈጥሮ ለሰው ልጆች እኩል የሰጠችውን መብት ከሰው ልጆች መለመንን የመሰለ ውርደት እንደሌለ ይገልጣል። የመብትና የነፃነት ልመናን የመሰለ ወራዳ አቋም የለም። W.E.B Du Bois The Souls of Black Folk በሚል ድሮ ባሳተመው መጽሐፍ “ተነሥ! የምታጣው ሰንሰለትህን ነው” ወደሚለው የተራማጆች ፍልስፍና ያመራል። እንዲያውም ሎወልን በመጥቀስ-
“Twixt old systems and the word
Truth forever on the scaffold
Wrong forever on the throne
yet that scaffold sways the future
And behind the dim Unknown
Standeth God within the shadow Keeping watch above His own”
ይላል። እውነት ዘወትር በመሰቀያው ሥፍራ፣ ውሸትና የማይገባው ሁሉ ዘወትር በዙፋኑ (በአልጋው) ላይ የመገኘቱ ነገር- ያ የመሰቀያው ጣውላ የወደፊቱን ሁሉ እየነቀነቀ መገኘቱ፣ እነሆ በጭላንጭሉ መሐል ደግሞ እግዚአብሔር ከፍ ብሎ ቆሞ የራሱን ወገኖች የማበረታታቱ ጉዳይ ዘላለማዊ ነው።
ልመለስ ወደ አሜሪካ ዓመታዊ የሰብአዊ መብት መግለጫ። ከላይ ያነሳሁአቸው የዱብዋ (አሜሪካኖች ዱባይስ ይላሉ ፈረንሳዮችን ለማብሸቅ) ወይም የፍሬደሪክ ዳግላስ ታሪኮች ለእነሱ ብዙ ይጥማቸው እንደሆነ አላውቅም። በተለይ ለሪፐብሊካኖቹ። እንደዚያም ሆኖ ይህ በእነሱ ድጋፍና ርዳታ ሞልቃቃ ሆኖ የተወለደውና የሚጨፍርብን ሥርዓት (መንግሥት) ፀረ ሕዝብ፤ ፀረ አገር፣ ፀረ እንጨት፣ ፀረ ሳር፣ ፀረ ሕዝብ፣ ለመሆኑ- እደግመዋለሁ- የእነሱ እማኝነት አለን። ጊዜው- የመለያያው- ደረሰና ነው ምሥጢሩን ሁሉ ያፈነዱት? ሊሆንም ላይሆንም ይችላል። እዚያ ላይ ያለውን ነጥብ የምንመለስበት ይመስለኛል። ለአሁኑ ግን አሜሪካ በአንድ በኩል ልትረዳን የምትችላቸውን ጉዳዮች ባነሳ- ከአንባብያን ድጋፍ ካገኘሁ።
አንደኛ- እስካሁን ድረስ አሜሪካ እንዲህ ያለ በሰብአዊ መብት አከባበር ረገድ የተበላሸ አቋም፣ በፖለቲካና በአገር አንድነት ጥበቃው ረገድ አሳፋሪ ሪኮርድ፣ በሕዝብ ሰላም ጥበቃና የፍትሕ መስተንግዶ መላሸቅ ረገድ ያልሆነላቸውን መንግሥታት ወይ Evil ኤምፓየር- ወይ Rogue State አለዚያም አሸባሪ (Terrorist) ሲሉ ባጅተዋል። ወያኔ ምንድነው? በእኛ ምደባ Terrorist Regime ሊባል ይገባዋልና ስያሜው በዚሁ እንዲሆን እንጠይቃለን።
ሁለተኛ፥ ይኸ ሁሉ ከተወሳና የወያኔዎች መንግሥትም ከሕዝብ የብድርና የርጥባን ገንዘብ 20 ቢሊዮን ዶላርስ ጠልፎ ወደግል ሂሳብ ያዋለ እንደመሆኑ- የዋና ዋና ሌቦችን የስም ዝርዝር እናቅርብና ወደየምዕራቡ መዲና ሲገቡ እንዲያዙና እንድንፋረዳቸው።- ገንዘባቸው እንዳይንቀሳቀስ እንዲደረግ- ከምዕራባውያን የሚሰጣቸው ማናቸውም ርዳታ ያለ ቅድመ ሁኔታ እንዲቋረጥ- ኢኮኖሚው ራሱ የተጠለፈና ወደ ግል ኩባንያነት የተዛወረ ስለሆነ የትኛውም አገር ከወያኔዎች ጋር የንግድ ልውውጥ እንዳያደርግ ዘመቻችንን እንዲቀበለን ትብብር እንጠይቃለን።- ከናይን ኢለቨን ጋር በተያያዘ አሜሪካ እንዳይደርሱ እግድ የነበረባቸው አንዳንድ ዘራፊና አቀባባይ ሌቦች እንደገና ወደ አሜሪካ ብቅ እያሉ የለመዱትን የሞራል ድቀት ትርኢታቸውን እያሳዩ ናቸው። ከእነዚህ መካከል አንዱን አረብ ግለሰብ የኢትዮጵያ ትውልድ ሁሉ የሚፋረደው ስለሆነ ተይዞ እንዲመረመር እንጠይቃለን። ወርቃችን፣ ሌሎች የማዕድን ሀብቶቻችን ወዘተ በዚሁ ሰው እንደ ትንሽ ዕቃ በየቀኑ እየተጫነ እንደሚወሰድ እናውቃለን። እናስረዳለንም። …………

በ1980ዎቹ Republic of Fear በሚል ርእስ ስለ ሳዳም ሑሴን ጨለማ አገዛዝ የሚያወሳው መጽሐፍ በእጅጉ ያሸማቅቃል። ጸሐፊው ኬናን ሜኪያ ይባላል። የኢትዮጵያ የዛሬ ሁኔታ ደግሞ ሌላ ባሕርይ ያለበት ይመስለኛል። ስለ ዋናዎቹ አምባገነኖች ሲነሣ አብዛኛዎቹ ነጠላ ናቸው። በቺሊ ፒኖቼ- በሩማንያ ቻይቼስኮ፣ በኢራቅ ሳዳም ሑሴን፣ በሊቢያ ጋዳፊ…ናቸው። ለወርቅ ጥጃቸው የማይንበረከክ፣ ለምስላቸው የማይሰግድ ከሁለት ስፍራ ይከፈላል። ያማቸው፣ ስማቸውን ያጐደፈ…የሚሰቃይበት አዳዲስ መሣሪያ አስፈልፍለዋል። ዝርዝር የማሰቃያውን ስልትና ድርጅት ከማእከላዊ ምርመራ ሠራተኛነት አምልጠው የወጡ ሰዎችን ማነጋገር ይቻላል። ባይሆን አንድ ጥያቄ በአእምሮአችሁ የሚመላለስ ወገኖቼ አትታጡም። መለስ ከሞተ በኋላም ይኸ አገር በአምባገነን የሚመራ ነው ለማለት ይቻላል ወይ? በእኔ በኩል ከሰዎች ጋር ስወያይ “አምባገነኑ የማይታወቅ አምባገነን መንግሥት” A Dictatorship without a Dictator ግን አገዛዙ መንጋ ጨካኖች፣ ነፍሰ- ገዳዮችና በዝባዦች ቢኖሩትስ? የፈረንሳዩ ታላቅ ምሁር ዣን ፍራንስዋ ሬቨል Without Marx or Jesus በሚለው መጽሐፉ እንዲህ ያሉትን አምባገነኖች ባሕርይ Collective Mediocrity and Collective bestiality ይለዋል። ነገሩ እንዲህ ነው። መለስ ሲሞት የእሱ እጓለማውታ (Orphans) መፈላለግ ያዙ። ሰብሳቢ አጣን ብለው ወደ ትካዜው ዓለም ተሰደዱና መጠራራቱን አንድ መፍትሔ አደረጉት። ምንጣፉን ቶሎ ብለው የረገጡት እነ እንቶኔ ደግሞ አራት ኪሎን የተጫጫነውና አሁንም የሚገዛውን መንፈስ በፍጥነት በማናቸውም አስማት ለማስወጣት አልቻሉም። ትንሽ ፋታ ሳያስፈልጋቸው አልቀረም። ጥቂት ጊዜ ከገዙ በኋላ የፕሮፓጋንዳውም መሣሪያ ትንሽ ትንሽ ይደፍረዋል። “መለስኮ ሰው ነው” ማለት ይጀምራል። ሰው መሆኑን ዛሬ ነው ያወቁት አትበሉአቸው። እኛ መለስን ከመቃብር አውጥተን አንፋረደውም። እነሱ ራሳቸው ከሳሽም ፈራጅም ይሆናሉ። ጠብቁ ብቻ።
በደርግ ጊዜ ስለአባካኝነትና አሻጥር ትልቅ ጉባኤ ተዘርግቶ ነበር። በንቁዝ (ኮራፕት) ባለሥልጣኖችና በመሳሰሉት ላይ ጥብቅና ወሳኝ የሆነ ርምጃ ስለሚወሰድበት ሁኔታ ውይይት ሲካሄድ በየቦታው ኮሚቴዎች እንዲቋቋሙ አሳብ ይቀርባል። በዚያ መድረክ ላይ የአገር አስተዳደር ሚኒስትር የነበሩት ጄኔራል ታዬ ጥላሁን የተናገሩት ትዝ ይለኛል። በአጤ ምኒልክ ዘመን እቴጌ ጣይቱ “ለአገሬ ለየጁ ያለው አንድ አፈንጉሥ ብቻ ስለሆነ ሌላ እንዲጨመርለት እጠይቃለሁ” ሲሉ እቴጌይቱን በአደባባይ ተቃውመው የማያውቁት ንጉሠ ነገሥት “እንኳን ሌላ ተጨምሮበት አንዱም ቢሆን አልተቻለም” አሉ ይባላል።
በዛሬዪቱ ኢትዮጵያ ከመለስ ሞት በኋላ አንድ ታዋቂና በአደባባይ ስሙና ሹመቱ የተገለጠ አምባገነን ባይኖርም ሟቹ በመጠኑ ራቅ ያደረጋቸው ሰዎች አልጋው ላይ የተረባረቡ ይመስለኛል። አቦይ ስብሐት፣ ጌታቸው አሰፋ፣ ዐባይ ወልዱ፣ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ወዘተ ወዘተ…በአንድ አገር የስለላው መረብ እንዳለ ወደ ፍጹማዊ ኅይል ሲለወጥ ደግሞ የዜጐች ሁሉ (መካከለኛ ደረጃ ያሉት ወያኔዎች ሳይቀሩ) መብት ወደ ኢምንትነት ይለወጣል። የሥነ መንግሥት ምሁራን በመንግሥት ውስጥ መንግሥት (ኤስቴት ዊዝን ኤ ስቴት) የሆነውን እንዲህ ያለውን ሥርዓት “መሪ” የሚባለውን ግለሰብ ጭምር ሽባ አድርጐ የሚቀፈድደው ያደርጉታል። በአሁኑ ሁኔታ ቀስ በቀስ የመለስ የቅርብ ሕዝብ አጫራሾች ዕጓለማውታ (ኦርፋንስ) ቢመስሉም ሌሎች በርካታ አምባገነኖች ጡንቻቸውን እያፈረጠሙ ናቸው። ወትሮ አንድ አምባገነን ያልቻለው የኢትዮጵያ ሕዝብ የብዙ አምባገነኖች ተሸካሚ ሆኖዋል። ሁሉም ነፍሰ ገዳዮች! ነፍሰ ገዳይ የማይፈራስ ማነው?
ለጊዜው በመንጋ ተንኮለኞች- ነፍሰ ገዳዮችና የዝርፊያ ሠራዊት እየተገዛን እንገኛለን። ስለእነሱ ድግስ፣ ስለ እነሱ ጥቅም፣ እነሱ የትኛዋን ጋለሞታ እንደሚጐበኙ፣ የትኛዋን መለኮን ዛሬ እንደወሰዱ እንወያያለን። በጥቃቅን ጉዳዮች አእምሮአችንን አስጨንቀናል። ወጣጥረነዋል። ይልቁን በሌላው ዓለም እየተቀጠቀጠ ማረፊያ ያጣው መንግሥታዊ አሸባሪነት የሙጥኝ ብሎ የሚገኘው በኢትዮጵያ መሆኑን እንተባበር። ይህን የሽብር መንግሥት ሌላው ቀርቶ በብረት መሞከርን ካህናቱና መነኮሳቱም መደገፍ አለባቸው። ከቶውንም ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በፋሺስቶች ጥይት ሊደበደቡ ጥቂት ሰከንዶች ሲቀራቸው “ልጆቼ ኢትዮጵያውያን ለፋሺስቶች እንዳትገዙ አውግዤአለሁ” ማለታቸው ይጠቀሳል። አዳዲስ ካሕናትና የዚህ ትውልድ ቀሳውስት ነገሩን ቸል እንኳ ቢሉ የአቡነ ጴጥሮስ ግዝትና ውግዘት አለብን። ቋሚ ነው- እስከማዕዜኑ።
ትግልና ታጋይ የሚጠይቁት አንድ ነገር ብቻ ነው። በደረትህ ውስጥ ጤነኛ ልብ፣ በጭንቅላትህ ውስጥ ጤናማ አእምሮ ካለህ ማናቸውም ችግር አይፈታህም። ጥይት አይመታህም። ድንፋታ ትርጉም አይሰጥህም። ቅጥፈትና ማስፈራራት ትጥቅህን አያስፈታህም። ልጆቼ ልላቸው የምችለው እነ እስክንድር፣ በቀለ፣ አንዱአለምና ርእዮት ይህን ወኔ በሰፊው የተቀዳጁ ናቸውና እንኮራባቸዋለን። እነሱ ወኅኒ ዓለም ሲገቡ የከዳናቸውና የቆሙለትን ዓላማ ጭምር የረሳንባቸው ከመሰላቸው ደግሞ አደራ በላነት ሊሰማን ይገባል።
ይህን ጽሑፍ የጀመርሁት በወያኔ የልደት በዓል ምክንያት ትንሽ የምለውን ለማቃመስ ነበር። ምናልባትም እንደ ፍሬደሪክ ዳግላስ ለእነዚህ ሰዎች “ጉንበት 20- ጉንበት ሃያ ትሉናላችሁ ጉንበት ሃያ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሥቃይ ሁሉ እናት የሆነችው ስቃይ የመጣችበት ቀን። ጉንበት 20 የባርነትና ወደር የሌለው ውርደት መታሰቢያ ቀናችን ናት። ጉንበት 20 ለእሥራታችን መታሰቢያችን ናት።” ልንላቸው እንችላለን። ይኸ የደፋሮቹ ጋዜጠኞች – የጀግኖቹ የፖለቲካ መሪዎችና ገበሬዎች የተባበረ ድምጽ ነው። በሬሳችን ላይ የሚጨፍሩበት፣ በመቃብራችን ላይ የሚያሽካኩበት፣ ቤትና ንብረት አሳጥተው ለስደት ያበቁንና በዚህ ደስታ የሚሰክሩበት በዓላቸው- የእኛ የልቅሶ ዕለት፣ የእኛ የመከራ ቀን መታሰቢያ ነው።
በመጨረሻም እንደገና ለአሜሪካ በማቀርበው ጥያቄ ላይ ይህችን ነጥብ እደግማለሁ። ይህ መንግስት ኢቭል የምትሉት አይነት ነው? ወይስ አሸባሪ? የወያኔ ኦሮሞዎች በኢትዮጵያውያን ኦሮሞዎች ላይ የሚፈጽሙትን እልቂት፣ የወያኔ አማራዎች (እነበረከት አምሮች ከተባሉ) በኢትዮጵያውያን አማሮች ላይ የሚያካሄዱትን መጠነ ሰፊ ድምሰሳ፣ የወያኔ ሙስሊሞች በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ እያደረሱ የሚገኙትን ወከባና ወደር የሌለው ጥቃት፣ ሟቹ የመለስ የሃይማኖት የይስሙላ ፓትርያርክና እንደ ሩሲያዊው ራስፑቲን የሚቆጠረው አባ ጳውሎስ በኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ያካሄደውን ሥቃይ አሜሪካ ከእኛ በላይ እንደማያውቀው ለዴሞክራሲ፣ ለሰብአዊ መብትና ነፃነት ስትል ርምጃ ለመውሰድ አቅዳለች? አጤ ኅይለሥላሴ በቀድሞው የመንግሥታት ማኅበር ጉባኤ ላይ ያደረጉትን ንግግር ለመጥቀስ እገደዳለሁ – “ታሪክና ትውልድ ፍርዳችሁን ይጠባበቃሉ!”
እነሆ ዛሬ በኢትዮጵያ የሰው ዘር ጠላት የሆነ ሥርዓት አለ። የሒትለርን ፀረ ሕዝብነት ለመረዳት የፖላንድ መወረር፣ የሃምሳ ሚሊዮን ሕዝብ ማለቅ፣ የስድስት ሚሊዮን አይሁድ መጨፍጨፍ መጠበቅ ይገባል? ታሪክ አላስተማራችሁምን? በአሜሪካ ላይ ስንት ክህደትና ቸልታ እንቁጠር? በፋሺስት ወረራ ዘመን ሩዝቬልትና ሴክሬተሪ ሐል ያሳዩን ክሕደትና ቸልታ አይረሳንም። አሜሪካ የበለጠ ትናገር! እግዚአብሔር ሁላችሁንም ይጠብቃችሁ!!

ህወሓት “ስሜን ልታጠፋ”ነው! (ከአብርሃ ደስታ)

$
0
0

ህወሓቶች ስሜን ለማጥፋት ዝግጅት መጀመራቸው የዉስጥ ምንጮች ገልፀውልኛል። ታድያ ቀጣዩ የመንግስት ሚድያዎች አጀንዳ ለመሆን ስለበቃሁ ህወሓትን የፈጠረ … ( ማነው የፈጠረው ደሞ?) የተመሰገነ ይሁን። እንዳዉም ሳስበው ለዓቅመ ትችት ደርሻለሁ ማለት ነው። ለማጥፋት ሚድያ የሚያስፈልገው ስም አግኝቻለሁ ማለት ነው። ስሜን ለማጥፋት ከተዘጋጁ ስም አለኝ ማለት ነው። ዕድሜ ለህወሓቶች! ለነገሩ ህወሓቶች ስም ያለውና የሌለው መለየት አይችሉም። እስቲ የሓሰት ውንጀላዎቻቸውን ለመስማት ያብቃን (ለነገሩ በቂሊንጦ ማረምያቤት ጀምረውታል አሉ)።

አብርሃ ደስታ

አብርሃ ደስታ

መስከረም አከባቢ ነው (ከዓረና ጠቅላላ ጉባኤ በኋላ)። አቶ አባይ ወልዱ ካቢኔያቸውን ሰብስበው “አብርሃ ደስታን መከላከል አንዱ የፖለቲካ አቅጣጫችን ነው” ማለታቸው ሰማሁ። በሚልዮን የሚቆጠር በጀትም መመደቡ ሰማሁ። ግን አላመንኩም። ምክንያቱም በጀት በመመደብ አብርሃን እንዴት መከላከል ይቻላል? ሰለማዊ ታጋይ ነኝ። ጠመንጃ የለኝም።

የሰማሁት ግን ብዙ ታማኝ የህወሓት ካድሬዎች ተመልምለው የፌስቡክ አጠቃቀም ሰልጥነው የአብርሃን ሐሳብ ማፍረስ እንዲችሉ ማብቃት ነበር። ግን የፌስቡክን አጠቃቀም መሰልጠን ሐሳብ ማመንጨት ማለት እንዳልሆነ ግልፅ ነው። እነዚህ የፌስቡክ ስልጠና የተሰጣቸው ታማኝ ካድሬዎች ሲጨንቃቸው በሓሳብ ከመከራከር ይልቅ መሳደብን መረጡ። በስድብ ሐሳብን ማሸነፍ ግን አይቻልም። እናም አልቻሉም።

እናም የተመደበው ገንዘብ ለታማኝ ካድሬዎቹ (የባለስልጣናቱ ቤተሰቦች) ተሰጠ። ሐሳብን ሊያመነጩ የሚችሉ ካድሬዎች በዝምድና ተመርጠው እንደየ አስፈላጊነታቸው በሑመራና ሌሎች ከተሞች መሬት በነፃ ተሰጣቸው (አርሶአደሮችን በማፈናቀል፣ ደግሞ አርሶአደር የት ይደርሳል? በረከተ ስምዖን ትዝ አለኝ)። ኢንቨስተሮች ሆኑ። ኢንቨስተሮች በመሆናቸው ህወሓትን አይተቹም እንጂ እኔም ለመንቀፍም ግዜና ፍላጎት አልነበራቸውም።

ከነዚህ መሬት የተሰጣቸው ካድሬ ኢንቨስተሮች አንዱ የግል ጋዜጠኛ ነኝ የሚል ሲሆን ባለፈው ሦስት ወራት በህወሓት መሬት እንዳልተሰጠው ሲምል ቆይቶ ዛሬ ግን በሑመራ መሬት እንዳለው አረጋግጦልኛል። እንዲህ ነው። ሰውየው ጋዜጠኛ ነው። በሑመራ አከባቢ የሚገኝ የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን በምስጢር መሰጠቱ ፅፌ ነበረ። ዛሬ አገኘኝና “የፃፍከው ስህተት ነው” አለኝ። “ስህተት ስለመሆኑ ምን ማስረጃ አለህ?” ስለው “እኔ ራሴ በሑመራ መሬት አለኝ። የኔ መሬት አልተወሰደም”አለ። ይገርማል። አንደኛ ከወራት በፊት በህወሓት መሬት ከተሰጣቸው ወጣቶች አንዱ እንደሆነ ነግሬው “ስህተት ነው። መሬት አልተሰጠኝም” ብሎኛል። ዛሬ የተበላሸበት ረስቶት ነው። ሁለተኛ በሑመራ ያለው የሱ መሬት ስላልተወሰደ ለሱዳን የተሰጠ የኢትዮጵያ መሬት የለም ማለት አይቻልም። ምክንያቱም መላው ሑመራ ለሱዳን ተላልፏል አልተባለም።

የህወሓት ፖለቲካ ስም የማጥፋት ፕሮፓጋንዳ ነው። ህወሓቶች የሰው ስም ብቻ አይደለም የሚያጠፉ፤ የሰው ህይወትም ያጠፋሉ። ይህን ሁሉ ተግባራቸው እናውቀዋለን። እናም በስም ማጥፋት ዘመቻ የሚሸበር የለም። ህወሓትን የምቃወመው መጥፎ ስለሆነ ነው። እናም በስም ማጥፋት ዘመቻ ተሰማርቶ መጥፎነቱን ቢያጋልጥ ህወሓትን የምቃወምበት ምክንያት ትክክለኛነት የሚያረጋግጥ በመሆኑ አይደንቀኝም።

አንድ አምባገነናዊ ስርዓት የሚፈፅማቸው ተግባራት ስም ማጥፋት፣ ማሰቃየት፣ ማሳሰር፣ መግደል ናቸው። ከዚህ ዉጭ ምንም ማድረግ አይችልም። ፍቅርን የማስፈን፣ ፍትሕን የማንገስ፣ እኩልነትን የማረጋገጥ፣ ስልጣንን ለህዝብ የማስረከብ፣ ነፃነትን የመስጠት ብቃት የለውም። ነፃነት ለመስጠት ብቃት ይጠይቃል። ሰው ለመግደል ግን ጠመንጃ መያዝ ብቻ በቂ ነው። ስለዚህ አምባገነናዊ ስርዓት የሚችለው ነገር መጥፎነት ነው። መጥፎ ስለሆነም ነው የምንቃወመው። ምክንያቱም የምንፈልገው መጥፎነንት ሳይሆን መልካምነት ነው። መጥፎ ተግባር በሌላ መጥፎ ተግባር ስለማይሸነፍ የህወሓት መጥፎነት በመልካምነት ለማሸነፍ እንሞክራለን። ምክንያቱም የምንታገለው ህወሓትን ለመተካት (ህወሓት የሚሰራውን መጥፎ ተግባር ለመድገም) ሳይሆን የህወሓትን የመጥፎነት ስርዓት በመልካም ህዝባዊ ስርዓት ለመቀየር ነው። የምንቃወመው ስርዓቱን ነው።

ምክር አለኝ! አሁን የታሰበው ስም የማጥፋት ዘመቻ በ2007 ምርጫ ወቅት ቢሆንላቹ ይሻላል። ምክንያቱም ዓላማቹና ሀይማኖታቹ ስልጣን ነው። ስለዚህ በምርጫ ወቅት ቢሆን መልካም ነው። ለማንኛውም ህወሓቶች መልካም ዕድል ብያለሁ (ለዘመቻው)። እንደ አኬልዳማና ሐረካት ለትዝብት የሚዳርጋቹና የሚያከስራቹ መሆን የለበትም።

ስሜ አይጠፋም። ምክንያቱም ስም የሌለው ስሙ አይጠፋም። ስም ለማጥፋት መጀመርያ ስሙ መኖር አለበት። አሁን ግን ስሙ የለም። ስም ለሌለው ሰው ስም ለማጥፋት የሚደረግ ዘመቻ ስም መፍጠር ነው የሚሆነው። ስለዚህ ስም ለማጥፋት ሲሉ ስም ይፈጥሩልኛል። እናም ይተውታል የሚል ግምት አለኝ። አጀንዳው የተነሳው እኔን ለማደናገጥ ታስቦ ሊሆን ይችላል።

It is so!!!

በደቡብ ኦሞ በ9 ቀበሌዎች የምግብ እጥረት ተከሰተ

$
0
0

የኦሞ ወንዝ (ፎቶ ፋይል)

የኦሞ ወንዝ (ፎቶ ፋይል)


በደቡብ ኦሞ ዞን በና ፀማይ ወረዳ 9 ቀበሌዎች ማለትም ሉቃ፣አይመሌ፣ሻላ፣ጎራ፣ቦላ፣ኦሎና፣ጊሽማ፣ጎኔ፣ኡፊ ቀበሌዎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚስፈልጋቸውና በአካባቢው የርሃብ ምልክቶች መታየታቸውን በደቡብ ኦሞ ዞን የአንድነት አመራሮች ለፍኖተ ነፃነት ገለጹ፡፡ ሻላ ጉያዮ፣ ቦላ፣ ኡፊ፣ ቦና፣ አይመሌ፣ ጊሽማ በተባሉት ቀበሌዎች ደግሞከፍተኛ የውሃ ችግር እንዳለባቸውም ታውቋል፡፡

በነዚህ ቀበሌ ውስጥ ያሉ አርብቶ አደሮች የዳልጋ ከብቶቻቸው፣ ፍየሎቻቸውና በጎቻቸው ሣርም ቅጠልም ማግኘት ስላልቻሉ እየሞቱባቸው ነው፡፡ ከየትኛውም ወገን ምንም ዓይነት ዕርዳታ ላገኙም ሲሉ በደቡብ ኦሞ ዞን የአንድነት አመራሮች አስረድተዋል፡፡ እነዚህን ወገኖች የሚረዱ በጎ አድራጊ ድርጅቶች በአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንዲያቀርቡላቸው በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች በፓርቲያችን ስም እንማፀናለን ሲሉ ገልፀዋል፡፡

በአካቢው ከጥር ወር ጀምሮ መዝነብ የሚገባው ዝናብ እስካሁን ባለመዝነቡ ከዚህም በኋላ ዝናቡን በመጠበቅ ሊከሰት የሚችለውን ችግር የከፋ እንደሚሆን የገለፁት የአንድነት አመራሮች እስካሁን የደ/ኦ/ዞ አስተዳደር ምንም ዓይነት እርምጃ እንዳልወሰደም በአካባቢውም የአደጋ መከላከልን ዝግጁነት መስሪያ ቤት የሌለ መሆኑንም ጭምር ገልፀዋል፡፡

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live