Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ሴቶች ጥሩ ነገር አላቸው ጊዜ እሲኪሰጣቸው ድረስ ጠብቀው ይይዙት ዘንድ እለምናቸዋለሁ።

$
0
0

ሥርጉተ ሥላሴ 21.12.2013

በሴቶች ስሜት ውስጥ መሆንና በስሜቱ ውስጥ ሴቶችን ሆኖ ማሰብ ከባድ ነው።

sreate1እኔን ተብድሬው አላውቅም። እኔንም ተውሼው አላውቅም። እኔንም ሸቅጬው አላውቅም። እኔንም መስዬው ሳልሆን ሆኘው ስለምጽፈው በስሜቴ ውስጥ ያሉ ነገሮች ሁሉ በአብዛኞቹ ሴት እህቶቼ ስሜት ውስጥ እንደሚኖር አስባለሁ። የድምፄ ምት ከማህጸኔ ይነሳል። የመንፈሴ ትንፋሽ ደግሞ የልቤን ክናድ ይንተራሳል። መንፈሴ ሰግሮ ሁነኛ ማረፊያ ወይንም ድልዳል ሲያጣ ትካዜ ሲዋኝበት የኖረ ቢሆንም፤ አሁን ከዘሃበሻ ጋር መታደሙ የመገለው ስቃይ ተግ ብሎለት ህምሙም ታግሶ፤ በስክነትና በቅደም ተከተል ማሰብና ከረመጥ ላይ የበቀለውን ጸጋ ማቆለማመጥ ጀመርኩኝ። ስለሆነም እኔ ራህብ ላይ ሆኜ ሌላ ራህብተኛ ለማስናገድ አቅሜን በሙሉ ቀን መርቆ የሰጠኝ አምላኬ፤ ምክንያት ፈጥሮ የመተንፈሻ ቀዳዳ ለፈቀደለኝ የዘሃበሻ ድህረ ገጽ ምስጋናዬን በሐሴት ጠልፌ ተቀበሉኝ በማለት እነሆ ጀመርኩኝ …

ሴቶች የመኖር ቋንቋ ናቸው። የኑሮ አይደለም። ኑሮ ቅርንጫፍ መኖር ግንድ። ውድ ወገኖቼ አጠቃላይ የነፃነት ትግሉን የአቅም ግንባታ፣ ጥበቃ፣ ያለውን ሃብት በቋሚነት ማዝለቅ እንዲሁም ስምሪት በተመለከተ ያላችሁበት በመሆኑ እሱን ተወት አድርጌ በዚህ ዙሪያ አንስት እህቶቻችሁ ያላቸውን ልዩ መክሊት አትኩሮት ብትሰጡት ሁሉም አካባቢ ያሉ ክፍተቶችን እንዴት ሊያበጅና ሊያሳምርም እንደሚችል በአላቸው  ዙሪያ  ትንሽ ነገር ለማለት ፈለግሁ። 

 

ሀ.       ሴቶች ችግርን ለመፍታት ቁርጠኝነት ጠረናቸው ነው።

 

የሴቶች ተፈጥሮ መግለጫ ከሆኑት መሰረታዊ ጉዳዮች እንብርቱ ሴቶች ችግርን የማይፈሩ ደፋሮች መሆናቸው ብቻ ሳይሆን ችግሩን ለመፍታት ቁርጠኝነትን በአጽህኖት የተካኑ ከመሆናቸው ላይ ነው። እንዲያውም ሴቶች ወስነው ችግር ወደ አለበት ፈጥነው የሚገሰግሱ መሆናቸው የተፈጥሯቸውን ብቃት ያመሳክራል። ስለዚህ ሴቶች ማናቸውንም ችግር ከቤት እስከ አደባባይ ያለውን ሁሉ አሳር ተዳፍረው ከመፍቻው ቁልፍ ጋር መፍትሄ የሚያስገኙ ድንቆች ናቸው። የፈለገ ዓይነት፣ በፈለገ ሁኔታ፣ በፈገ መጠን፣ በፈለገ ጊዜ፣ በፈለገ ግንኙነት፣ በፈለገ ልኬታ፣ ችግር በቅሎ ይጠብቃቸው አብዛኞቹ እንደ አመጣጡ መክተው፣ መንገዱን ጠርገው ለጥ ያለ አስፓልት በማድረግ፤ ወጣ ገቡን የሚታድጉ የመፍትሄ ማሃንዲሶች ናቸው። አቅርቧቸውና ፈትኗቸው ወኔው ካላችሁ ….

 

ለዚህ ማገናዘቢያ ይሆን ዘንድ …. እኔ በተመስጦ የኩርድሽ ሴቶች የጫካ ትግል እከታተላለሁ። ወንዶች ከተማ ሆነው የሎቢ ተግባር ይሰራሉ፤ ሴቶች ጫካ ሆነው የጀግንነት ግሩም ድርጊት ይከውናሉ። ጦር አዛዧ ሴት፤ የግንኙነት ኃላፊዋ ሴት፤ የሎጅስቲክስ ስምሪት አስተዳዳሪዋ ሴት፣ የጓድ መሪዋ ሴት፣ አዝማች ሴት … ወዘተ  ከትንግርት በላይ ነው። ጥንካሬያቸው፣ ብርታታቸው፣ ትብብራቸው፣ ጽናታቸው፣ የጫካ ህይወት ፍቅራቸው ንዑድ ነው። አምላኬን የምለምነው እንዲህ እንደ ጨው ዘር የተበተነውን ለእነሱ ቅንነት ሲል እንኳን በጉልበተኞች የተወሰደባቸውን መሬት አግኘተው ለሀገራቸው እንዲበቁ ነው። የአርበኝነት ውሏቸው ሰው መሆንን ይመረምራልና። ዓላማችውን አሳክቶ፤ አርበኛነታቸውን ለፍሬ አብቅቶ መሬት አልባነት ከትሞ እማዊ የተግባር ሰውነት ምን ያህል ፍሬ ስለመሆኑ በ21ኛው ምዕተ – ዓመት በዓለም ዓቀፍ ዕውቅናውን እንዲያስጌጥ የዘወትር ፀሎቴ ነው።

 

ለ.       ሴቶች ስልት ተፈጥሯቸው ነው።

 

የሴቶች የአያያዝ ጥበብ በስልት ነው። ስልቱ ደግሞ ሩቅ ዓላማን ሰንቆ የቅርብ ፍላጎትን ሳይዘል አስማምቶ፣ አስመችቶም የመከወን ጠንካራ አቅም አላቸው። አሁን የቅርብ ምሳሌ ባነሳ በሳውዲ ላይ የተፈጠረው ችግር ጊዜያዊ መፍትሄ ለመስጠት መረባረቡን ሴቶች ከልብ ያምኑበታል። ነገር ግን ይህ የመከራ ዘመን የሚመክንበት ጉዳይ ላይ በርትቶ መስራትን ያሰምሩበታል። ለዚህም ዕድሉ ቢኖራቸው ቅደም ተከተል ሰጥተው የአቅም ክፍፍሉን አሳምረው ይቀይሱታል እንጂ ሳቢያዎች በሚፈጥሩት ውጤቶች ላይ ብቻ ጊዜያቸው እንዲበላ አይፈቅዱም። በፍጹም። ነገም ሌላ ችግር በባሰ እንደሚበቅል ጠንቅቀው ያውቁታል። ስለሆነም አትኩሮታቸው በሳቢያ ላይ የሚያጠነጥን ብቻ ሳይሆን ይልቁንም በምክንያት ውጤቶች ላይ የተሳላ ነው። ተግባባን?

የችግሩ መፈልፈያ ከምንጩ መድረቅ አለበት። መነቀል አለበት – የሥራዓት መሰረታዊ ለውጥ ላይ አብዝቶ ከተሰራበት አብዛኞቹ የዛሬ ችግሮቻችን በሂደት በራሱ ጊዜ ያስተካከለዋልን።

ሐ.      የሴቶች ቀድሞ የመተንበይ አቅም ዓይነታ ነው።

 

አንድ ጊዜ በ90ዎቹ አጋማሽ ውጭ ሀገር አንድ የሥራ ባልደረባዬ፤ አለቃችን ሳይኖር አለቃዬም ነበር ለነገሩ  አዛውንት ጋዜጠኛ ታዋቂ በድንገት ሞቶ ቀብሩ ላይ ነበርኩኝ። አስከሬኑ ተቃጥሎ በትንሽ ነገር መያዙን አላስተዋልኩትም ነበር። እኔ እምጠብቀው ሳጥን ስለነበረ ከአጠገቤ ላላው ባልደረባዬ የተግባር መምህሬም ነው፤ መቼ ነው አስከሬኑ የሚመጣው? ስል ጠዬኩት ሂደቱን አጫወተኝ። ባለቤቱ የውጭ ዜጋ እንደ ሆነች እንደ እምነቷ፣ ቦታም ገንዘብም ለመቆጠብ እሬሳው እንዲቃጠል መወሰኗን አብራርልኝ። ይህን አሰቃቂ  ትዕይንት ስሰማም፣ ሳይም የመጀመሪያ ቀኔ ስለነበር አካባቢው እራሱ ቀፈፈኝ። ከአጠገቤ ደግሞ አንዲት አበባ የመሰለች ውብ ሴት እጅግ አምርራ ታለቅሳላች። ወደ እሷ ዞር አልኩኝና ጠጋ ብዬ እንድትታገስ ነገርኳት። ከዛ ምን እንዳለችኝ ታውቃላችሁ“ለራሴ ነው የማለቅሰው“ እንዴት? ስል ጓጉቼ ጠዬኳት። ለዛውም ሰው ፈቅዶ ካልነገረኝ ስለምንም ነገር መጠዬቅ አልወድም።

 

… ብቻ ጠዬኳት „ እኔ ተሰደድኩ፤ የስደቱን ፈተና ስላልቻልኩት የውጭ ዜጋ አገባሁ፤ ወለድኩኝ። አዬሽ አይደል መመለሻ የለኝም፤ አስከሬኔም የሀገሬ አፈር አያገኝም – በሁለት ምክንያት። ቀድሜ ብሞት ባለቤቴ የሚያደርገው ይህንኑ ነው። እንደ ባህሉ ያቃጥለዋል። ልጆቼም በዚህ ውስጥ ስለሚያድጉ ያፀድቁለታል አለችኝ“ ምንም እንኳን ሁሉም ጋብቻ ላይ ይህ ባይደርስም ዛሬ ላይ ሆኜ የትናት ትንበያዋን፤ ያ ሁለቱ የተፈጥሮ መስኮቶቿ ተከፈተው ገድቡን ጥሶ ሙላቱን ይለቀው የነበረው ፍላሎት ዛሬ ላይ በምልሰት ስቃኘው ሚስጢሩ ተገለጠልኝ። ሴቶች ነገን የማየት አቅማቸው ብጡል* (ጥንካሬው የደመቀ ልዩ) ነውና። ይህን ዘመን በድርብ ስመዝነው ደግሞ አይደለም ውጪ ሀገር … ሀገር ውስጥም መሰሉ ሊፈጸም እንደሚችል ምልክቶች ይጠቋቁማሉ። አስፓልቶች የኢትዮጵያ መሬት አይመስሉም፤ የገጠር መንደሮችም እንዲሁ …. ተወራላች ሀገራችን …. ውርርሱ የመሬት ብቻ ሳይሆን የዕምነት አፈጻጸም የተጋደመ ባህልም … እንዳይሆን ስጋቴ ነው።

 

… በዛው የቀብር ሥርዓት ያቺ ፔርሙስ በምትመስል ሰፋ ባለች ጎድጓዳ ማህል እጅ ላይ ተቀምጣ የነበረችው አዬኋት። አፈሩ ጫረጫር ተባለላትና እንደ ሀገሬው ባህል ወጉ ደራሳት። መሬቷ አንድ ስንዝር ብትሆን ነው። ያን ዕለት ከጎኔ ላላው ለማከብረው የቅርብ አለቃዬ ጠጋ አልኩና እኔ ደግሞ „በሰው እጅ የሞተ ይመስለኛል አልኩት።“ በጣም ፍጥነት የተሞላበት ነገር ነበር የተመለከቱት። እሱም “እናንተ ሴቶች መቅደም ተፈጥሯችሁ ነው። አብረን በኖርንባቸው ወቅቶች የታወቀ ምንም ዓይነት በሽታ አልነበረውም። ሁልጊዜም የህክምና ቁጥጥር ያደርጋል። ባለቤቱን ስለሁኔታው ደውዬ ስጠይቃት በመረጋጋትና  በአሸናፊነት መንፈስ ነበር ያጫወተችኝ። አሁን አንቺ ይህን ስትይ ግን የተሰወረ ግን ልንድርስበት ያልቻልነው ነገር አለበት ብዬ አስባለሁ። ለዚህም ይሆናል ብቻዋን ወሰዳ እንዲቃጠል ካስደረገች በኋላ የቀብር ሥርዓት ላይ ብቻ እንድንገኝ የነገረችን“ አለኝ። ከዚህ ላይ እኔ ትንቢተኛ ነኝ ለማለት አይደለም። ሴቶች ደራሽ ችግሮችን በተለያዬ አቅጣጫ እንደሚያዩት ለማጠዬቅ እንጂ …

 

ወገኖቼ … ሴቶች እንደ ወረደ የሚያስተናግዱት ምንም ነገር የለም በፍጹም። ይበልቱታል። የበለቱትን ክፍል ሰጥተው ይደለድሉታል። የደለደሉትን ንክኪና ግንኙነት ያላቸውን ነገሮች ሁሉ ከአገናኙ በኋላ ይፈታትሹታል በዬ አቅጣጫው፣ በዬዞኑ። ፍተሻው ጠንከር ያለ የበራ ፊድ ባክ ወይንም ምላሽ ይሰጣቸዋል። ያ ፊድ ባክ ወይንም ምላሽ ዕርገታቸውን ያሳካላቸዋል …. እህታችሁን፤ የትዳር አጋራችሁን፤ እናታችሁን ለናሙና ወስዳችሁ መመዘን ይቻል ይመስለኛል።

 

መ.      ሴቶች በተፈጥሯቸው የተደራጁ ናቸው።

 

በሙያዬ አደራጅም ስለነበርኩ ብዙ ሳልጓዝ ብዕሬ በተወሰነ ጉዳይ ላይ ብቻ እንድታጠነጥን እለምናታለሁ። የሴቶች የመደራጀት ሂደት ከዬት የሚጀምር ይመስላችኋል። ከማህል? ከጠርዝ? ከማዕዘን? ከቀኝ – ከግራ – ከፊት – ከበስተኋላ? የሴቶች መደራጀት የሚጀመርው ከመንፈሳቸው አስኳል ነው። እንቅስቃሴያቸው „ሀን“ ዘሎ „ለን“ አይጀምርም – በፍጹም። እራሳቸውን አደራጅተው ነው የሚኖሩት። የሴቶችን እንቅስቃሴ የሚመራው በተደራጀ፣ በተሰናዳና በተከወነ መንፈስ ነው። ስለዚህ ከመደራጀት የሚገኘው ዕሴት ሁሉ ተጠቃሚ ናቸው። በዓለም የመጀመሪያው የድርጅትን ዋጋ አውቆ ጥቅም ላይ የዋለ ፍጥረት ቢኖር ሴቶች ናቸው። በሴቶች ህይወት ውስጥ ምን ያልተዳረጀ ነገር አለና? ስለሆነም አቅማቸውን በሥርዓት መርተው ለአቀዱት ዓላማ ጥቅም ላይ በአግባቡ ያውሉታል /ኢንቤስት/ ያድረጉታል …. ኃይላቸው ብክነት የለበትም። የፍሬ ነገሩ ኩላሊት ያለው ተዚህ ላይ ነው። ኃይላቸው ጥግና መጠለያ ምንጊዜም አለው። አሁን በዚህ የነፃነት ትግል የሚባክነውን ገንዘብ? ጊዜ? የሰው ኃይል ቁጭ ብዬ ሳዬው የነፃነት ራህብተኛ ነንኝና እከስላላሁ … እንደ እኔ ሚሊዮኖችም …. አቅም እኮ አድመጭ ያጣ ቅምጥ ሃብት ነው። ለነፃነት ትግሉ ግን ጆሮም የለም ጊዜም በኩርማን ተቆንጥጣ … ለዛው ከተገኘ … በጠብታ ….

 

ሠ.       የድምጽ እንቁጢ የሴቶች መክሊት።

 

ሰሞኑን አንድ ሁለት መጣጥፍ ላይ ስለ ድምጽ አንስቻለሁ። ተወቅሸበታለሁም። እሱን በደስታ አስተናግጄ … በሰለጠነው አለም እኮ ድምጽ የሚሰለጥኑበት ሙያ ነው። ድምጽ ከምንም ነገር በላይ ቀልብን የመግዛት ሙሉ አቅም አለው። አዎን እኔ ሥርጉተ የውብ ድምጽ ቃና ፍቀረኛ ነኝ። አውዳለሁም። ነፃነት መጋፋት ኃጢያትም ወንጀልም ነው። በነፃነት ሀገር ነፃነቴን ማንም እንዲነጥቀኝ አልፈቅድም። ስለሆነም ነው የታሰረውን እዬተጋልኩ ተስፋ ሳልቆርጥ በተገኘው አጋጣሚ የምተነፍሰው። የተሰበረ ሞተር ወይንም ኮሳሳ ወይንም የሩጫ ፍልሚያ የሚጋብዝ ፋታ ነሽ ወይንም የታፈነ …. ለታላቁ የነፃነት ጉዞ አልመኝለትም። ምን በወጣው ….? በራሱ የሚተማማን፤ እውነትን የተንተራሰ፤ ለህግ የበላይነት የቆረጠ ዓለምን የሚየስደምም ኢትዮጵያዊነትን የሚታደግ ባለ ግርማ ሞገስ ድምጽ ናፍቆቴ ነው … እንዲመራኝ።

አሁን ወደ ቀደመው ነገር እንደ አቨው ….ካለ ዓመት የማትመጣው ብሄራዊ አበባችን እንቁጣጣሽ። እንቁጢ ተናፋቂ ናት። እንቁጢ ተስፋ ድውለቷ ነው። እንቁጢ አዲስነት ቅልጥሟ ነው። እንቁጢ ፍቅር ብርንዷዋ ነው። ታጥቦ የፈጠራት፣ ተናፍቃ ትመጣላች ሳትጠገብ ደግሞ ሽው …. እሷን ባደረገኝ።

የሴቶች ድምጽም እንቁጢ ነው። ድምፃቸው በደመቀ – በለሰለሰ – በሰከነ  – ልዩ ቃና የጣፈጠ ነው። ደወሉ የመንፈስ ድህነት ነው። ምቱ … የተዘጋ ይከፍታል። የታመመ ይፈውሳል። ተስፋን ላጣ በገፍ ተስፋን ይቸራል። የደከመን ያበረታታል። የጎበጠን ያቃናል። መፍቻ ያጠን ያፍታታል። ምን የማይሆነው አለ? የሴቶች ድሪያማ ውብ የርህራሄ፣ የቸርነት፣ አበረታች ለስላሳ ቀለማም ቅላፄ ይጠጣል።  ይጎረሳል። ይዋራረዳል። ያሰግራል። ያፍለቀልቃል። ያጽናናልም …. ይብቃ አይደል ወራጅ አለ በሉኝ።

ለማንኛውም ይህ ሃብት ግን ከቁጥር የማይገባ … ከፋይዳ የተዘለለ፤ ከመርኃ – ግብር የተፋቀ የተረሳ ጸጋ ነው። ዘንቦ ተባርቆ የሚዲያ የራዲዮ ሆነ የቴሌቪዥን ሰራተኛ ካልተሆነ ምክንት አብዝቶ የሚጨፍርበት አንጡራ ሃብት። በዬትኛውም ቤታ የአሸናፊነት መንገዱ ሁሉንም አካባቢ ዳስሶ በታቀደና በተደራጀ ሁኔታ በመንቀሳቀስ ኢትዮጵያዊነትን መታደግ ሲቻል … ፀጋው ውሃ ሲሄድበት የከረመ አለት ሆኖ ኤሉሄ አሉሄ ይላል …. ሞገዳማ ተንቀሳቃሽ ድምጽ የአጥቂነት ትጥቅ፤ የአሳማኝነት በትረ ሞገድ ነበር ላወቀበት ግን እንዴት? የታነቀ እውነት ….

 

ረ.      እናትነት።

 

ይህ እንግዲህ ለተባዕት የተከለከለው መንገድ የራሳችን ብቸኛው አንጡራ ሃብት ነው። ተቀናቃኝን በራሱ ጊዜ የመከተ። በፌክም ከማስመሰል በስተቀር መሆን የማይቻልበት ለሴቶች ብቻ የሰማዩ ዳኛ መርቆ የሰጠን የጸጋዎች እጬጌ ነው።  እናትነት የድርብርብ ፍቅር ክታብ። እናትነት በልቡ ውስጥ ልብ። የእናትነት ነገር ሲነሳ ወላዊና አውንታዊ እድምታ ላይ እንደርሳለን። እናትነት ሚስትነት ነው። የጡት ባህረ መዝገብ ሲገለጥ እናትነትን ከነክብሩ ይመጣል። ፍቅር ይከተላል። እናትነትን ሚስጢር የሚለው ቃል ሊገልጸው የሚችለው አይመስለኝም። የተከደነ ታምር ወይንስ የገድላት ቅዱስ መጸሐፍ ልበለው። እናትነት አይደለም ለሰው ልጆች እንሰሳ ላይ እንኳን ሲታይ ታምሩን የሰው ልጅ በጥበቡ ሁሉ ያልደረሰብት መክሊት ነው። እናትንት በተን ግን ጠቅላል ያሉ ሰንደቃዊ ቃሎችን ወይንም ኃብታቱ …

አለሁነት …. መቅድምነት …ቤተሰባዊነት … ታማኝነት … ተሳታፊነት …ቅርብነት … እቅፍነት …ተከታታይነት … አቀራራቢነት … አቀናባሪነት …ቀጥተኝነት … ዕንባመነት …ማራኪነት … ቻይነት … መሪነት … ሃላፊነትን በፈቃድ መውሰድ … ርህርህና … ስብዕዊነት … ሚዛናዊነት … ፍቅር … ቅንነት … አዎንታዊነት … አርቆ አሳቢነት … መምህርነት … ማህበራዊነት … ታማኝነት … ግልጽነት … ቀጥተኛነት … አድናቂነት … አክባሪነት … ተንከባካቢነት …. ኪዳንነት …. ለችግር ቀድሞ ደራሽንት … አጉራሽነት … አጽናኝነት … እውነትነት … ፈጣንነት … ባለሙያነት …. መሪነት …  አስተዳዳሪነት … መስዋዕትነትን ፈቅዶና ቆርጦ ተቀባይነት … አደራጅነት … አስተባባሪነት … ተጠያቂነት … ለጋስነት … ቸርንት …. አድማጭነት … አዛኝነት … ፈቃደኝነት … ቀዳሚነት … ኑሮነት …. ሁለመናነት … የሁሉዬነት …. መሆንነት … ሎሌነት …። በጣም በእርግጠኝነት እናት ለልጇ፣ ለትዳሯ፣ ለወገኗ፣ ለኃላፊነቷ ሁሉ ሎሌ ናት።

እያንዳንዱ ሥነ ተፈጥሯዊ ገፀ ባህሪ ደግሞ የራሱ ጭብጥና አምክንዮ አለው። እንደ እራሱ የመኖር ነፃነትና ከሌሎች ጋርም በመፈቃቀድ የሚያስተሳስረው ወርቃዊ ሃዲድም አለው። ድንበርና ወሰንም። ይህ ተፈጥሯዊ የገነት ህይወት ያለው የጸጋ ጅረት የራሱም ሥነ ምግባር፣ የራሱ አርትና ጣዕም አለው። ዬራሱ ዜማና ቃና አለው። የራሱ ማንነትና መግለጫ አለው። የራሱ አናትና ልብ አለው። የራሱ ፋይዳና ዕሴት አለው … የራሱ መተዳደሪያ ደንብና ሰነድም አለው። ይህ ሁሉ ተዝቆ የማያልቅ ጥሪትና እምቅ ቋሚ ሃብት ተዘሎ ይታቀደላል ሁል ጊዜ ግን ታቱ ዥግራ …

 

ሰ.      ሴቶች ብልህነት ወስጣቸው ነው።

የሴቶች ጸጋ ልጥፍ አይደለም። ከውስጣቸው በመሆን ያታተመ እንጂ። ሴቶች እጅግ ሲባዛ ብልሆች ናቸው።  በእያንዳንዱ የዓለም ታዋቂ ወንድ በሉት፤ ጀግና – ሳይንቲስት በሉት፤ ተመራማሪ በሉት፤ ተወዳጅ መሪ፤ በስተጀርባ አንዲት ብልህ ሴት በቅርበት አለች። አብዛኛውን ጊዜ የትዳር አጋራቸውን የሰሙ፤ ያዳመጡ፤ የተከበሩ መሪዎች ሆኑ፤ ለሽልማት የሚበቁ የስኬት ቁልፋቸው በእጃቸው መኖሩን ይቀበሉና ያረጋጋጡ ። እርማጃቸውን አንድ ብለው ከመጀመራቸው በፊት። የሁሉም ነገር መፍቻ ስልትና ብልሃት የመዳፋቸው እርእስና እርስት ሆኗልና እንኳንም ደስ አላቸው። የንጉሦች ንጉሥ የአፄ ቴውድሮስ ጠቅላላ ታሪክ በዛ መልክ የተጠናቀቀው እቴጌ ምንትዋብ በሞት ስለተለዮዋቸው ብቻ ነበር እንጅ እቴጌ በህይወት እያሉማ ድል በድል እዬተነባባረ የአሸነፊነትም የመሪነቱ እርክን አንቱ ነበር። እስከ እስራኤል ድረሰም ነበር ምኞታቸው።

እቴጌ ጋር የዐጤው መንፈሳቸው በድል ሰረገላ ላይ ያሸበሽብ ነበር። እቴጌ ለንጉሡ መዳህኒት ነበሩ ….  በብልህነት ሴቶች ተዝቆ የማያልቅ ፍጹም ልዩ ሥጦታ ነው ያላቸው። ደግሞም ስልታቸውን ተክትሎ ለሚጓዝ ህልሙ ቅርብ ነው። ድሉም ከፊት ለፊቱ ….

እስቲ ጠይቁልኝ እርቃ ሳትሄድ

እቴጌ ተዋበች ሚስትናት ገረድ

እጅግ „ሥራ አዋቂ“ ትናንትና ሞተች

መዳህኒቱን „ምሳ“ ታበላኝ ነበረች።

/ምዕራፍ 19 ከዐፄ ቴውድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተክለ ጻድቅ መኩሪያ መጸሐፍ የተወሰደ።/  እጅግ „ሥራ አዋቂ“ ይህ ኃይለ ቃል የሴቶች ሥነ – ተፍጥሮ ተግባር ስለመሆኑ ብቻ ሳይሆን ዕውቀታዊ – አንስታዊ ውስጥንም አሳምሮ ይገልጠዋል። ሴቶች ለቧልት ጊዜ የላቸውምና። ሁለተኛው „ምሳ“ ታበለኛለች የሚለው ሰምና ወርቅ ነው። ሰሙ የማዕከላዊ የምግብ ክፈለ ጊዜን ማዕደኝነት ሲገልጽ፤ ወርቁ ሁለት ጥንድ ትርጉምን ይዟል። አንደኛው ቀደም ባለው ጊዜም ሆነ አሁን በገጠሩ ሀገረ-ሰብዕዊ መዳህኒቶች ከተክል ሥር ወይንም ከዕፅ ተቆፍሮ የሚገኝ ስለመሆኑ፤ ዶሱ ወይንም መጠኑ በጣት ተለክቶ እንደ ዕድሜው መሰጠቱን ይገልፃል። ስለዚህ ዐፄ ቴወድሮስ ህምም ሲሰማቸው ፈርማሲያቸው፣ ሃኪማቸው ከቤታቸው ነበሩ – እመቤት እቴጌ ምንትዋብ። ሌላው የወርቁ መጠነ ሰፊ ክፍለ አካል በዘመናችን ቁብ ያልተሰጠው ፍሬ ዘር ወይንም ነገረ ሚስጢር ግን ዐፄ ቴውድሮስ በንግሥና ዘመናቸውም ሆነ ሃሳባቸውን ሲወጥኑት ከልጅ ካሳነት ዘመናቸው ጀምሮ አስተዳደራዊ ብቃታቸው  ከእቴጌ ይቀዳ እንደነበር ለማጠዬቅ ነው።

በሌላ በኩል የአልጋቸው ጽኑ ጠባቂ የፕሮቶኮል ሹማቸው አማካሪያቸው እቴጌ መሆናቸውን ያመሳጥርልናል። ከዚህ ላይ የጉዳዩን ኩላሊት ከልብ ስንፈታትሽው ደግሞ ቀደምት ንጉሦቻችን የሴቶችን ተፈጥራዊ ልክ የማይወጣለት ብቃት ለመዳህኒትነት፣ ለችግር መፍቻነት፤ ለጭንቅ መበተኛነት፣ በአግባቡ ጥቅም ላይ ያዋሉና በዚህም ፈውስና ድህነት ማግኘታቸውን ቁልጭ አድርጉ ያስተምረናል ….

ከዚህ ጋር በተያያዘ የደህንነት እና የልጅነት ሚስጢርን በእናትነት ፀጋ ጎልምሶ የምናዬው ክፍል ደግሞ እቴጌ ሲሞቱ  …. የነበረውን አብረን እንመልከት።

እቴጌ ለባለቤታቸው አድልተው ወደ ትዳራቸው ፍላጎታቸው ቢመዝንም፤ እንደ ቤተሰባዊ ጸጋቸው በሴት ልጅነታቸውም አባታቸው በነበሩበት የግዞት ዘመን ሁሉ ከጎናቸው ነበሩ፤ ትዳራቸውን ሳያስከፉ በጥንቃቄ የልጅነት ድርሻቸውን በስውር ተወጥተዋል። ሊደረግላቸው የሚገባውን ተግባር ሁሉ አድርገዋል። እጥፍ ጸጋ። ሴት ልጅና ወንድ ልጅ ለወላጆቹ እኩል ተግባር ላይ አይገኙም። በቤተሰብ አያያዝና ክህሎትም ቢሆን  እኩል የመሆን አቅም የላቸውም - ፈጽሞ ። ለዚህ ነበር ራስ ዐሊ ልጃቸውን ሞት ሲነጥቅባቸው …. እንዲህ ብለው ቅኔውን የዘረፉት …. የጎደለ ሞይነት – ሁለመናነት … ሁሉዬ ሴት!

 

ጠጅ አማረኝ ስላት ማሩን ትሰዳለች (ለተጠማ ሆነ ለአምሮት ደራሽነት)

ራበኝም ስላት እኽሉን ታስጭናለች (ለራህብ ፈጥኖ ደራሽነት)

በረደኝም ስላት ሸማ ትሰዳለች      (ለታረዘ አልባሽነት)

ሌባዬ ተይዛ ባልጋ ትሄዳለች        (የድህንነት ጥበቅ ተግባር በስውርና በጥበብ)

የት አባቷን ዐውቃ ታሳዝነኛለች    (ችግርን ተጋሪ ሲርቅ ረመጥ ስለመሆኑ)

የጣቴን ቀለበት አንተ አድርገው ካሳ (ኪዳንህን ጠብቅ አደራ፤ ጽና!)

በኔማ ጣት ገብቶ አስጨነቀኝሳ (የሃዘኑ ቋያ ረመጥ ልኬታ አለመኖሩን) ያመላክተናል

( ከዐፄ ቴወድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከተክለ ጻድቅ መኩሪያ መጽሐፍ ገጽ 20) የተወሰደ

ሴት ልጅ – እናት፤ እህት – ጓደኛ – አክስት –  ስትሆን ሚስጢሩ ሆነ ትርጉሙ ጣና ዘገሊላ ነው ….. ዛሬስ አቶ ወንዶች ይህን የማመሳጥር አቅም አላችሁን?

 

ሸ.      ሴቶች የተረጋጋ መንፈስ።

 

ይህ የሴቶች ተፈጥሮ ተግባር ላይ የሚውለው በትዳራቸው፤ በእናትና ልጅ ዙሪያ ወይንም በስብዕዊነት ዙሪያ አይደለም። ስለምን? በዚህ ዙሪያ ለሚመጡ ሰቀቀኖች ሴቶች ስሜታቸው ስስ ነውና። ነገር ግን ኃላፊነትን በሚጠይቁ የመወሰንን የመቁረጥ ሂደቶች፤ ሂደቶችን ተከትለው በሚመጡ አጣብቂኝ ፈተናዎች ዙሪያ ሴቶች የሰከነና መሬት ያዬዘ የተረጋጋ መንፈስ አላቸው። በመጀመሪያ ነገር ጉዞውን ሲጀምሩትም በአመዛኙ ይመጣል ብለው ካላሙት ችግር ውስጥ ያፈነገጠ አይሆንም። ስለሆነም በታቀደ እንቅስቃሴ ውስጥ የተጠበቀን ፈተና ለማስተናገድ ሴቶች ተረጋጋግተው የማስተናገድ ሆነ የመራመድ አቅማቸው ማገር – ፒላር ነው። በተፈጥሮ ሊቅነት። … ሥጦታው በትምህርት በተመክሮ ሲታክልበት እንዲሁም የተከበረ ተደማጭነት ሲያገኙ … መስፈርቱን ሆነ ዕሴቱን ለመለካት አይችልም … ዝልቅ ነዋ!

 

ቀ.      ማስተዋል ሴቶችን ይገልጣቸዋል።

 

ሴቶች አጋጣሚዎች የሚመራቸው ፍጥረቶች አይደሉም። ወይንም ሴቶች አጋጣሚን ተጠልለው አያቅዱም። መርኃ ግብራቸው እራሱን የቻለ እና ግብታዊነት የማይመራው በመሆኑ አትኩሮታቸው በጭብጡ ማዕክላዊ ዙሪያ ስለሚሆን ለግቦች ቅርብት ሆነ ለውጤቶች አስተማማኝ ግብዕት ናቸው። የሴቶች የፍላጎት ትልም ለወጀብ ሆነ ለአውሎ የተጋለጠ አይደለም  … እሳተ ጎመራን የመቋቋም ብቃቱ መካች ነው።

 

በ.      የሴቶች ነፃነት ናፈቂነት፤

 

ይህ የሴቶች በኽረ ህልም ነው። ምክንያቱም ውስጣቸውን ጠንቅቀው ስለሚያውቁት ድርሻቸውን ለመወጣት ተድቦልቡሎ ግን ተስውሮ የሚፈታታናቸውን የትምክህት ቲወሪ የሚመክት ነፃነት ይሻሉ። ለዚህ ነፃነትም ትርጉም ያለው፣ ድርጊተኝነትን በማስቀድም በግንባር ቀደምትነት ይጋፈጣሉ። እርግጥ ዘመንና ጊዜ የሚጠበቁ ነገሮች እንዳሉ ቢገነዘቡም፤ አጋጣሚዎችን ሳይዘሉ የምልክት ደወል መደወላቸውን ግን አያቋርጡም። ከናፍቆታቸው ጋርም ለመገናኘት ተግባር እንደሚያሸንፍ ስለሚያምኑ ድምጻቸውን አጠፍተው ከድርጊት ጋር ይባትላሉ – ይመስናሉ … በታሪክ ጊዜ የሌላቸው ቢዚ ፍጥረቶች ቢኖሩ ሴቶች ናቸው። በሁሉም ቦታ በተጫነ ጉልበታም ትምክህት ሥር ወድቀው፤ ግን ተሳትፏቸውን በትጋት ይወጣሉ። ፈተናው ሲጠናባቸው ሲስፈልግም ዞር ወይንም ለቀቀ አድርገው ግን ቀዳዳ ፈልገው ይተጋሉ። እንግሊዘኛው ስለሚገልጽልኝ ሙሉ ፓኬታቸው ትንታግ ነው – ። ለዚህም ነው ዕርሴ መጠበቅን ጽላቱ በማድርግ ሴቶች ጥሩ ነገር አላቸው ጊዜ እሲኪሰጣቸው ድረስ ጠብቀው ይይዙት ዘንድ  እለምናቸዋለሁ ያልኩት።

 

ጠቅለል ይበል …

 

የተፈጥሮ ውብ ዘላቂ ጥሎሽ የሴቶች ብቃት ነው። ዝም ብዬ ቁጭ እልና ሴቶችን ፊት ለፊቴ አስቀምጬ ሁለመናቸውን እፈትሸዋለሁ። እንደ ሰርጀሪ ነገር …  ሁለመናቸውን አስተውለዋለሁ። እያንዳንዱን ቅመማዊ ተፈጥሮ እዬነጠልኩም አናግረዋለሁ። ሁለመናቸውን እዬተነተንኩም እመካበታለሁ። ሁለመናቸውን እያፍታታሁ እጽናናባቸዋለሁ። ሁለማናቸውን እያስተዋልኩ አደንቃቸዋለሁ። ሁለመናቸው እዬዳሰስኩ እበረታታባቸዋለሁ – እውዳቸዋለሁም። ሁለማናቸውን በዓይኔ ወስጥ አስቀምጬ መንፈሴ እንዲደለው ፈቅጄ ነገን አልመበታለሁ። ቀደም ባለው ጊዜ „ እረኛ ምን አለ“ ይባል ነበር። አሁን ሰሞኑን የኢትዮጵያዊነት ስሜትን ፍላጎትን ሳወጣና ሳወርድ ከአንድ ጥቅል ፍላጎት ላይ ደረስኩ“ጣይቱ“ የሚለው አዲሱ  የአንስት ወላዊ፣ ትንቢታዊ፣ ፍላጎታዊ፣ ፈቃዳዊ፣ ጠያቂያዊ … ዜማ … እርገቱ በታዳጊ ወጣት የተስፋ ጠቅላይ ሚ/ር ቃለ ምልስልስ ሲጠናቀቅ ጨዋው ህዝባችን፤ ፈረኃ እግዚአብሄር ያለው ህዝባችን፤ ለእምነቱ ዶግማና ቅኖና ሞቱን የሚመርጠው ህዝባችን አንድ ነገር መንፈስ ቅዱስ እንደ አቀበለው ልብ አልኩኝ …. እንኩይ ….. የናፈቀው የሰከነ ፖለቲካዊ አመራር ከአንስት ነውና …

 

ከዚህ ጋር በተያያዘ ደግሞ መራኂት አርቲስት አለምጸኃይ ወዳጆ „የጣይቱን የሥነ – ጥበብ ማዕከል“ አሜሪካን ላይ አደራጅታ ጥበብን ተጠዬቅ ስትል፤ ቀድሞ የታያት ወርቅ እንደነባራትም ተገለጠልኝ። …. እሷም እኮ አለች … የጀመሪያው የተውኔት ባላሙያዎች ማህበር ብሄራዊ ሊቀመንበር … አስታዋሽ አርቲስት ታማኝ ባጠገቧ በመኖሩ ምክንያትም ቢሆን ኢሳት ይመስገን ተዚህ ላይ። … በሶስተኛ ጉባዔው ላይ ገላጭ አድርጓት አይቻለሁ፤ ግን ይህ በቂ አይደለም … ማስታወሱ መልካም ሆኖ ግን ሩቅ መጓዝ፤ ትብትቡን ፈቶ ቅኔዊ ውስጧን በቋሚነት ጥቅም ላይ መዋል ይገባል … ስብሰባ እኔ የምተረጉመው ገብያ በማለት ነው።

 

እናቴ ስትነግረኝ በልጅነቷ ጓደኛ ታበዛ ነበርና መሞታቸውን አውቀው፣ ሰኔልና ቹቻ አዘጋጅተው፣ ልጆቻቸውን መርቀውና ተሰነባተው ጸሎት ቤታቸው በሰላም ያረፉት ሊቀ – ሊቃውንቱ አያቷ መላክ ብርኃን ልሳንወርቅ ኃይለ ሥላሴ ቤተሰብ „ገብያነሽ“ ያላትን ስም አስቀሩት። ስለምን ገብያ ተሎ ይፈታል። ልጄ ዕድሜዋ ተግባሯም አጭር ይሆናል በማለት ሌላ ድንቅ ስም አወጡላት። አሁንም ሰው ወዳጅ ስለሆነች ተከባ ተከብራም አለች በባዕቷ። ምን ለማለት ነው እጅግ የፍቅሯን ንጥር ቅቤ ጠጥቶ ባደገው የልቤ ሙዳይ ውስጥ ብቸኛ ቦታ የሰጣት መራኂት ዓለምጸኃይ ወዳጆ … ቶሎ ለሚፈታ ጉባዔ ብቻ አትታጭ ዘለግ – ዘለቅ፤ ትርጉም ላላው ተሳትፎ፤  አቅሙ ጉልበታም ለሆነ የኃላፊነት ቦታም ትታሰብ እንላለን … እንጮኃለን …. ተፈጥሮ እንዲያምርበት ማጣፈጫ አምላክ ፈጠረለት ሴትን።

 

ሉሲ የ21ኛው ምዕተ ዓመት የሰው ልጅ ምንጭ ሆነች … ሳይንስም የኢትዮጵያዊነትን ሚስጥር ሳይነቅፍ ከሃቅ ጋር እርቀ ሰላም አወረደ። አመሳጠረ። ታዲያ ድንቅነሽ ማለት እኮ ሴት ናት … ተዚህ ማዕከል ይኮንና በኩነኔ ተፈርጆ ገሃንም የተወረወረው የሴቶች ብቃት ባሊህ ይባል እንላላን። የተከረቸመው በርም ይነቅነቅ እንላላን ///  እኔና የተከበረችው ብዕሬ – መንፈሴም ይታከል ….  ከዓውደ ምህረቱ ሆኖ  እንቢልታውን እያስነካ ውስጡን ላከ … ለጆሮ ….

 

ለነበረን የመደማማጥ ሸጋ ጊዜ ኢትዮጵያዊ ዘንካታ ምስጋና አቅርቤ ለዛሬ ልሰናበት። ቸር ያሰንብተን፤ ቸር ያሰማን አምላካችን አሜን።

 

ሴቶች የድርጊት ጀግኖች ናቸው!!!!!

የሴቶች ተሳትፎ በማለት የሰከረ ሳይሆን መሆንን የሰነቀ ነው!!!!

 

ይቅርታ በትህትና አክብሮትም ታክሎበት አንዳንድ ቦታ ላይ እንግሊዘኛውን ቃል ወስጃለሁ፤ ውስጤ አቅም አንሶት አይደለም ፍላጎቴን የበለጠ አስረግጦ የሚገልጸው እንግሊዘኛው ሲሆንብኝ ነበር … ትንሽ ዲቃላ ነገር የሆኑት ገለፃዎቼ …

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

↧

↧

ጥቁር ነኝ … ነገር ግን ውብ ነኝ

$
0
0

ሙሉጌታ አሻግሬ

mulugetaashagre@yahoo.com
ማህበር እየደገሰች ዘመድ የምትሰበስበዋ አክስቴ ‘አገር የጋራ ነው ሃይማኖት የግል ነው’ ትላለች። ይህን አባባል ለአክስቴ መስጠቴ አይደለም ሙስና እንዳይሆንብኝ። ህዝቡ ሁሉ እንደዛ ይላል። አክስቴ ምን ታድርግ መስመርና አብዮት የተባሉ ሰው ሰራሽ ጭራቆች ወንድሞቿን በልተውባታል። ይህ አባባል በፖለቲካ ምክንያት እሳት እና ጭድ የሆኑ ቀሪ ዘመዶቿ የተለመደውን ንትርክ እንዳይጀምሩ የምትጠቀምበት ዘዴ ነው። እኔ ግን ስተረጉመው ‘ዝምድና የጋራ ነው ፖለቲካ የግል ነው’ ማለቷ ነበር። በአክስቴ እምነት ፖለቲካ ጥሩ አይደለም። ሞት ያስከትላል።
ግን ሃይማኖትና ፖለቲካ እውነት ለየቅል ናቸው? ይህን አስተያየት ለመፃፍ ያነሳሳኝ ሰሞኑን አንድ ወዳጄ ጀባ ያለኝ የስብከት ሊንክ ነው።

ምንም እንኳን እንደአባባሉ ሃይማኖት የግል አገር የጋራ ቢሆንም የወያኔ ገዥ ቡድን አገርም የእነርሱ፤ ሃይማኖትም የእነርሱ እንደሆነ ህቅ እስኪለን ድረስ አሳይተውናል።
የእስለምና መሪዎች ሹመት በቀበሌ ምርጫ ካልሆነ ምኑን ሃይማኖት ሆነው ሊሉን ዳርዳር ያሉ የወያኔ ካድሬዎችን ታዝበናል። ማንን ፈርተው እንደተዉት ባይታወቅም ‘የመጅሊስ ተመራጮች ምርጫ ቦርድ መመዝገብ አለባቸው’ የሚል የደደቢት ቀጭን ትዕዛዝ ይተላለፋል ብዬም ጠብቄ ነበር። ኦርቶዶክሱንም ቢሆን ያልተመቻቸውን ሽረው፣ የተመቻቸውን ሾመው ፣ ኽረ ወግ እየተናደ ነው ብለው ቅሬታ ያሰሙ አባቶችን ደብድበውና አስደብድበው ሲኖዶሱ የእነሱን መስመር የሚከተል እንዲሆን ሰርተዋል። በአደባባይ በመውጣት ሚዲያ በመጠቀምም የኦርቶዶክስን አከርካሪ ሰብረናል ብለዋል። ስለዚህ ፖለቲካ ከእኛ በላይ ለአሳር ያሉት የወያኔ ገዥ ቡድን አባላት ይህን ካደረጉ እና ከተናገሩ፤ የእኔ የተራው ዜጋ ሁለት መስመር አስተያየት ሃይማኖት እና ፖለቲካን እንደማታቀላቅል እጅግ እርግጠኛ ነኝ።
ስብከቱ ከአንድ ሰዓት በላይ ነው። ትዕግስቴ አፍንጫዬ ላይ እንደሆነ የሚያውቀው ወዳጄ ግን አዳራ ጨርሰህ እንድትሰማው ብሎ መክሮኝ ነበር፤ አይገርምም አንዴ አይደለም ደግሜ ሰማሁት። በዚህ አስተያየት ውስጥ የሃይማኖት ክፍሉን ለሃይማኖቱ ተከታዮች በመተው ወቅታዊ የአገሪቱን ችግር የተመለከተውን ብቻ ለማሳየት እሞክራለሁ። የሰባኪውንም ማንነትም ሆነ የሃይማኖትን ጉዳዮች ሳልነካካ ማለት ነው። የወዳጄም ትልቁ ፍላጎት ይህ ነው።
ሰባኪው ይናገራል። በጥንቱ መፅሐፍ ቅዱስ እያጣቀሰ የኢትዮጵያን የዛሬ መከራ እና ችግር ይተረትረዋል። ወጣትነት፣ ስደት፣ ሙስና ፣ አድልዎ፣ ተጠያቂነት ምንም አልቀረውም። ሰባኪው የቤተክርስትያኗን አንደበት የሸበበውን በረዶ ሰብሮታል። ልክ ‘ICE Breaker’ እንደሚባለው ማለት ነው። ይህ መጀመሪያው ነው፤ አምናለሁ በርካቶች ሊከተሉ እንደሚችሉ እርግጠኛ ነኝ። አሸባሪ ተብሎ ክስ ካልተመዘዘበት በቀር። ግን ደጋግሞ ‘መናገር ካለብኝ እናገራለሁ፣ አልፈራም ’ ይላል ሰባኪው።
ወያኔ ድሮም በሃይማኖት ጣልቃ የመግባት ምስጢር መንግስተ ሰማያት አሊያም ጀነት የመግባት ፍላጎት አሳስቦት አይደለም። ወያኔ የኢትዮጵያን ህዝብ ያውቀዋል። ኢትዮጵያዊው በሃይማኖቱ ስነምግባርን ብቻ ሳይሆን መስዋዕትነትም የተማረ ህዝብ ነው። ስለዚህ ወያኔ ስልጣኑን ለማስጠበቅ ትላልቅ የሚባሉ ሃይማኖቶችን ወደራሱ መንገድ መጠምዘዝ ነበረበት። ህዝቡ የሃይማኖት አባቶችን ፣ የእምነት ተቋማቱን ያዳምጣል። ከልቡ። ስለዚህ ወያኔ በዚያ በኩል ሊመጣ የሚችለውን ‘የስልጣን አደጋ’ ለመከላከል የዘየደው ዘዴ የሃይማኖት ቁንጮዎችን ማወየን አሊያም መቆጣጠር ነበር።
እንደስብከቱ ግን ሃይማኖትን በአግባቡ ለማምለክ አገርና ማንነት ያስፈልጋል የሚል ግልጽ መልዕክት ተላልፏል። አትዝረፉ። ኽረ ሙስና ይብቃ።ተጠያቂነት ወዴት ነሽ? እያለ ሰባኪው ይጠይቃል። በቃ፣ በቃ፣ ይበቃል። ይላል ሰባኪው። ወያኔዎች በዚህ መልኩ ከተረዱት ትምህርት ይወስዳሉ። እራሳቸውንም ከጥፋት መልሰው ህዝቡን ማዳመጥ ይጀምራሉ። ይህን መልዕክት የትምክህተኞች እና ያለፈ ስርዓት ናፋቂዎች ነው ብለው የተለመደውን ነጠላ ዜማ ከለቀቁ ግን ከእግራቸው ስር ያለው መሬት እየተሰነጠቀ መሆኑን ለመረዳት እንደረፈደባቸው ያሳያል።
ህዝቡ በሃይማኖት በኩል ማጉረምረም ከጀመረ …. ኦሮማይ።
ጥቁር ነኝ … ነገር ግን ውብ ነኝ
ሰባኪው በክሊፑ ከ18፡00 እስከ 19፡15 ስደትን እየነገረን ለሚደርሰው ግፍ እና ኢሰብዓዊ ድርጊት ተጠያቂ የለም ይለናል። ከ 28፡33 እስከ 29፡35 ስለ ኢትዮጵያውያኖች ጀግኖች፤ ስላልተዘመረላቸው የኢትዮጵያ እንቁ ጀግኖች ይጠይቃል። ይናገራል። የእኛ ጀግኖች ብዙ እንደሰሩ ግን እንደተደበቁ ያስታውሰናል።
ከ42፡20 ጀምሮ ስለ ኢትዮጵያ ጥቁር ህዝብ ማንነት ይናገራል።የኦርቶዶክስን አከርካሪ መስበር ኢትዮጵያን ለመስበር መሞከር እንደሆነ በማስረጃ ይተነትናል። ቤተክርስቲያኗ ትምህርት ቤት፣ የህክምና ቤት፣ የፍርድ ቤት እንደነበረች ይነግረናል። አከርካሪዋ መሰበር ሳይሆን መመስገን ይገባታል ይለናል።
ከ46፡50 ጀምሮ ስለ ሞራል፣ ስለ አገር ተረካቢነት ይጠይቃል። ሙስና ከቤተመንግስት እስከ ቤተክህነት መንደሯን በስፋት እንደሰራች በግልጽ ይነግረናል። ህዝቡን እርስ በእርስ የማበላላት ፕሮግራም የኢትዮጵያን የወደፊት ማንነት ጥያቄ ውስጥ እንዳስገባ በመጠየቅ፤ መብላት እና መበላላት መወገድ አለበት ይላል። አጽንኦት በመስጠት።
ከ58፡30 ጀምሮ ሰባኪው ወደማንነታችን እንመለስ ይለናል። ወደ እውነት እንምጣ ይለናል።እምቢ፣ እምቢ እንበል ይለናል፤ ኢትዮጵያውያኖች ነንና። ኢትዮጵያውያኖች ነንና ነውር የሆነውን ትተን ወደክብራችን እንመለስ ይለናል።
ከ 1፡00፡50 ጀምሮ ስለነፃነት አባቶች ፣ ከባርነት ላወጡን አርበኞች ክብርና ምስጋናውን ያቀርባል።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

↧

የጥራት እና ደረጃ መዳቢ ባለስልጣን መ/ቤት እና ሕ.ወ.ሓ.ት (ልዩ ትንታኔ)

$
0
0

ጥራት እና ደረጃዎች
ነጻነት ይበልጣል (ከጀርመን)

tplfዛሬ ላስነብባችሁ ያሰብኩት  ቀደም ሲል የጥራት እና ደረጃዎች መዳቢ ባለስልጣን መስሪያ ቤት ተብሎ ይጠራ ስለነበረው  አሁን ለአራት ተከፋፍሎ እንዲጠፋ ስለተደረገ ተቋም ነው፡፡ መስሪያቤቱ ምርት እና አገልግሎችን  በመቆጣጠር የሸማቹን ደህንነት እና ጤንነነት ማስጠበቅ ፤ የገቢና ወጪ ምርቶችን  ጥራት በመከታተል ጉልህ ድርሻ እንዲያበረክት ታስቦ የተቋቋመ ነው፡፡ መስሪያቤቱን ለረጅም ዓመታት በበላይነት ይመሩ የነበሩት አቶ መሳይ ግርማ ሲባሉ በውስጡ የፍተሻ እና ካሊብሬሽን አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የሰርተፊኬሽ አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የኢንስፔክሽን አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የደረጃዎች ዝግጅት ዳይሬክትሬት፣ የስልጠናአገልግሎት  ዳይሬክትሬት እና የፋይናንስ ዳይሬክትሬት እና ሌሎች የአገልግጎች ዘርፎች ነበሩት፡፡አቶ መሳይ መስሪያቤቱን ከ16 ዓመት በላይ አስተዳድረዋል፡፡ ድንገት ባልተጠበቀ ሰዓት ከአቶ መሳይ እውቅና ውጭ 3 ሰዎች  አቶ ተክኤ ብርሀኔ ከመቀሌ፣አቶ ደቻሳ ጉሩሙ ከጅማ እና አቶ ዳንኤል ዘነበ ከሀረርጌ ተመልምለው  ወደ መስሪያቤቱ ተመደቡ፡፡

ሰዎች ሳይፈለጉ መመደባቸው ብቻ ሳይሆን በወቅቱ እንዲከፈላቸው የተፃፈላቸው የደመወዝ መጠንም በመስሪያቤቱ የደመወዝ ስኬል የሌለ፤ ካላቸው የትምህርት እና የስራ ልምድ ጋር ምንም አይነት ዝምድና ስለሌለው አቶ መሳይ መክፈል አልችልም በማለት አንገራገሩ፡፡ እነሱ መች የዋዛ ቢሆኑ እና እስከ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተዘረጋ ሰንሰለት ስለነበራቸው በስልክ ተደውሎላቸው ሳይወዱ በግድ መክፈል ጀመሩ፡፡ እነዚህ ሰዎች በ2002 ዓ.ም ለሚካሄደው  ምርጫ ቅድመ ዝግጅት እንዲረዳ ከየክልሉ ተፈልገው የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ሀዋርያ ሁነው ወደ ፌዴራል መንግስት የመጡ ናቸው፡፡ተክኤ በስፓርት ፣ደቻሳ በሂሳብ እና ዳንኤል በማኔጅሜንት ተመርቀዋል፡፡ ሲመጡ የሚያርፉበት የኪራይቤቶች የሚያስተዳድረው ሰፋፊ ግቢ የተዘጋጀላቸው ሲሆን ዳንኤል ከአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጽ/ቤት አጠገብ፤ተክኤ እና ደቻሳ ደግሞ 22 አካባቢ ባለ ሰፋፊ ግቢ እንዲኖሩ ተመቻችቶላቸዋል፡፡

ዋናው  የቅርብ ጊዜ አላማቸውም በ2002 ለሚደረገው ምርጫ የመንግስት ሰራተኛውን ከኢህአዴግ ጎን ማሰለፍ እና ቀጣይ አመራሮችን ማዘጋጀት ነው፡፡ በዚህም መሰረት ባሉበት ቀበሌ በምርጫ ጣቢያ ሀላፊነት ተመድበው ይሰራሉ፡፡በተጨማሪም መንግስት በቢ.ፒ.አር.(business process re engineering) ብሎ ወደፊት ሊዘረጋ ላቀደው የሰራተኞች ማፈኛ መንገድ የራሱን  ታማኝ  የስለላ ሰዎች ወደ መሲሪያቤቱ ያስገባል፡፡ የአዲሶቹን ተመዳቢዎች አመጣጥ ተከተሎ በመስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የፍረሃት  ድባብ ተፈጠረ፡፡እነሱ ሰራተኞችን ወደሚጭነው ሰርቪስ ሲገቡ አንድም ሰው ትንፍሽ አይልም፡፡የአውቶቡሱ ሰው ሁሉ በጸጥታ ይዋጣል፡፡ጆሮ ጆሮ እያሉ ያንሾካሽካሉ፡፡ በእረፍት ሰሀት እነሱ በተቀመጡበት አካባቢ አብሮ ተቀምጦ ሻይ ቡና የሚል የለም፡፡ሲመደቡ የኮሙኒኬሽን ሰራተኞች ተብለው ሲሆን ከመስሪያቤቱ እውቅና ውጭ ከነአቶበረከት ሰምኦን ጋር በየሳምንቱ ስብሰባ እና የመረጃ ልውውጥ ያደርጋሉ፡፡ከሳይንስና ቶክኖሎጂ ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲን ሳዶ ጋር ከፈለጉ በአካል መኪና አዝዘው ካልፈለጉ በስልክ በቀጥታ መገናኘት ይችላሉ፡፡

አቶ መሳይ እና ሌሎች የመስሪያቤቱ ከፍተኛ አመራሮች የማያውቁት መረጃ ከነሱ ጋ ይገኛል፡፡በዚህ የአንድ አመት ቆያታቸው በመስሪቤቱ ደጋፊዎችን ማፍራት አልቻሉም፡፡

በ2003ዓ.ም የቢ.ፒ.አር ጥናት ሲጀመር አዲስ የመጡት ካድሬዎች  የጥናት ቡድን መሪ እየተባሉ ተመደቡ፡፡ ቢ.ፒ.አር ለመስራት ቀርቶ ስለመስሪቤቱ አሰራር በቂ እውቀት የሌላቸው ሰዎች መስሪያቤቱን አፍርሶ እንደ አዲስ የማደራጀት ስራ በእነዚህ ሰዎች ስር ወደቀ፡፡በዚህም ተቀራራቢ ስራዎችን በጋራ ማደራጀት በሚል ሰበብ ከብሄራዊ የጨረር መከላከያ አንዱን መምሪያ በማፍረስ፤የክሊነር ፐሮደክሽን መስሪያቤትን ሙሉ በሙሉ፤የሳይንስ መሳሪያዎች መስሪያቤትን ሙሉ በሙሉ አፈራርሰው አነዚህን መስሪያቤቶች ከደረጃ መዳቢ ባለስልጣን መስሪያቤት ጋር በማዋሀድ አራት የተለያዩ መስሪያቤቶችን ለመፍጠር ጥናቱ ተጀመረ፡፡ አዲስ የተጠኑት መስሪያቤቶች

1.Meterology institute,

2.Accreditation biro,

3 .Standards agency

4. Conformity assessment enterprise ይባላሉ፡፡

እነዚህ መስሪያቤቶች በተጠኑበት ወቅት ለጥናት ቡድኑ በየሳምንቱ በጣም ውድ በሆኑ ሆቴሎች የእራት ግብዣ  እየተዘጋጀ ለ6 ወር ያክል ተደከመበት፡፡ወደ መጨረሻው ምእራፍ ሲቃረብ  የጥናት ቡድኑ ሙሉ በሙሉ ናዝሬት ውስጥ ከ10 ቀን በላይ ሆቴል ውስጥ ተቀምጠው እንዲሰሩ ተደረገ፡፡በመጨረሻም የጥናቱን መጠናቀቅ አስመልክቶ  በአቶ ጁነዲን ሳዶ አማካነት አርባምንጭ ለሶስት ቀናት ድል ያለ ግብዣ ተደረገ፡፡ከአርባምንጭ መልስ ሁሉም በሳይንስ እና ቴክኔሎጂ ሚ/ር ስር የሚገኙ ሰራተኛ  ለገሀር በሚገኘው የመንገድ እና  ትራንስፖርት መሰብሰቢያ አዳራሽ ጠቅላላ ስብሰባ ተካሄደ፡፡በስብሰባው የየጥንት ቡድኑ ሀላፊዎች የጥናታቸውን ውጤት ይፋ አደረጉ፡፡የሀገራችን ችግሮች ተዳሰሱ፡፡ለችግሮች መፍትሄ ይሆናሉ የተባሉ አማራጮች ከየአቅጣጫው ጎረፉ፡፡

አብዛኞች ወጣቶች ተስፋ ያደረጉትን በየመስሪያቤቱ ያለውን ብልሹ አሰራር እንዴት ማስወገድ እንደሚቻል አስተያየታቸውን ሰጡ፡፡በዚህ ውይይት ከተነሱት ውስጥ እስካሁን የማሰታውሳቸው አቶ ገብረጊዳን ገብረመስቀል በቅጽል ስሙ(GG) “በየመስሪያቤቱ ያለውን የተማረ የሰው ሀይል  እጥረት ለመቅረፍ መንግስት በውጪ የሚኖሩት ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ገብተው እንዲሰሩ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ለምሳሌ እንደ ኢንጅነር ቅጣው እጅጉ አይነት ሰዎች ነበሩዋት ሌሎችም እንዲህ አይነቶች ይኖራሉ ብሎ ተናገረ፡፡”በእረፍት የንግድ ሚኒስትሩ የአቶ ታደሰ ሐይሌ ባለቤት ወ/ሮ አልማዝ ካህሳይ ይህን የተናገረውን ልጅ ጠራቸው እና ስሙን ጠይቃ “አንተማ የእኛው ነህ እየውልህ ኢ/ር ቅጣው በመንግስታችን ላይ ሊሰራ አቅዶት የነበረውን ስለማታውቅ ነው እንዲህ ያልከው፡፡በቶሎ ቀጨው እንጂ ቢቆይ በጣም አደገኛ ነበር፡፡እንዲህ አይነቱን ሰው ስሙን መጥራት የለብህም” አለችው፡፡

ይቅርታ ወ/ሮ አልማዝ እኔ እሱን አላውቅም ነበር ሲል መለሰላት፡፡ሌላው ከጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት የመጣ  አቶ ጸጋዬ የሚባል አንድ ተናጋሪ በንግግራቸው መሀል ጣል ያደረጉዋት ቀልድ መሰል መልክት ሁሌም ትከነክነኛለች፡፡አቶ ጸጋዬ “አማርኛ እጅዋን አገኘች በግል ትምህርት ቤት ውስጥ አማርኛ መናገር እና ድንጋይ መወርወር ያስቀጣል ተብሎ በጉልህ ተጽፎ አንድ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ አንብቤያለሁ” ብለው አረፉ፡፡ ሌላው ጠያቂ አብዲ ዱጋ ይባላል፡፡አብዲ ጥያቄውን ያቀረበው ለሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ነው፡፡ጥያቄው “ኦሮሚያ ክልል ውስጥ አየተካሄደ ያለው የአበባ እርሻ ልማት የአካባቢውን አፈር እና ውሃ እየበከለው ነው፡፡በዚህም የተነሳ እንስሳት ይሞታሉ ሰዎች ይታመማሉ፡፡የሰራተኞችም ህይወት አደጋ  ውስጥ ነው  የሚከፈላቸውም ገንዘብ እዚህ ግባ የሚባል አደለም፡፡እንዲያውም  ባለ ሀብቶች ከሌሎች ሀገሮች ሲባረሩ ነው ወደዚህ ሀገር የመጡት ይባላል እና ይህን እንዴት ያዩታል? ሲል ጠየቀ፡፡አብዲን የገጠመው ከፍተኛ ውግዘት ነው፡፡ለውግዘቱ መነሻም በወቅቱ የአበባ እርሻ ልማት ሲጀመር አቶ ጁነዲን የኦሮሚያ ርእሰ መስተዳድር ስለነበሩ እሳቸውን እንደተቃወመ ተቆጠረ፡፡አብዲም ያጠናው ባዮሎጂ ስለነበር ሙያዊ ትንታኔ መስጠቱን ቀጠለ፡፡ክርክሩ እየከረረ ሲሄድ ጓደኞቹ ዝም እንዲል አደረጉት፡፡ስልጠናው ለ5 ቀናት በፍረሃት እንደተዋጠ ተጠናቀቀ፡፡ከዚህ ሰብሰባ መልስ በቀጥታ ሁሉም መስሪያቤት ወደ ሰው ኃይል ምደባ እንዲገባ መመሪያ ተላላፈ፡፡

Woyanes shoud face justice

ስብሰባው አርብ ተጠናቆ ሰኞ ጠዋት አቶ መሳይ ከመስሪያቤቱ በፍቃዳቸው እንዲለቁ  ትእዛዝ እንደተሰጣቸው  ለሚቀርቡዋቸው ሰዎች  ሲናገሩ የኮሚኒኬሽን ሰራተኞቹ እነ ተክኤ ደግሞ  ምደባውን እንዳያስተጉዋጉል በማሰብ አስቀድሞ መባረሩን በየቢሮው እየዞሩ ያውጃሉ፡ይህን ተከትሎ መስሪያቤቱ ሰው የሞተ ያክል በኡኡታ በልቅሶ ታመሰ፡፡አብዛኖች መልካም ተግባሩን ለሰራተኛ አዛኝነቱን እያሰቡ አባታቸውን በሞት የተነጠቁ ያክል ከልብ አዘኑ፡፡በዚሁ እለት የንግድ ሚኒስትሩ የአቶ ታደሰ ሀይሌ ባለቤት ወ/ሮ አልማዝ ካህሣዬ መስሪያቤቱን እንዲያስተዳድሩ ተሾሙ ፡፡የተለያዬ ዳይሬክተሮችን ሹመት ሰጡ፡፡በዚህ ወቅት ቀደም ሲል ወያኔን እንደሚቃወሙ የሚታወቁት እና ከአቶ መሳይ ጋር ቀረቤታ አላቸው የተባሉ ነባር ዳይሬክተሮች ተነስተው በምትካቸው የኢህአዲግ አባላትን መመደብ ተጀመረ፡፡ ምደባውም የሚካሄደው እያንዳንዱ ሰራተኛ እየተገመገመባለው ችሎታ ነው ይባል እንጅ ነገር ግን አስገራሚው እና ያን ያክል የተደከመበት ጥናት የግምገማውን 75% የሚይዘው  ከስራው ጋር ምንም ግንኙነት የሌለው አመለካካት የሚባል ነገር ነው፡፡ሰራተኞች በወቅቱ ያነሱት የነበረው ጥያቄ አመለካከት በምን ሊለካ ይችላል የእኔን አመለካካት ምን እንደሆነ ማን ያውቀዋል የሚል ነበር፡፡

ግምገማውን የሚሞሉት ቀደም ብየ የጠቀስኳቸው እነ ተክኤ፣ደቻሳ እና ዳናኤል ናቸው፡፡እነዚህ ሰዎች እንደመሰላቸው የግምገማ ነጥቡን መስጠታቸው ሳያንስ ምደባውን በዋናነት የሚመሩት እነሱ ናቸው፡፡ወደ ደረጃ መዳቢ መስሪያቤት የመጡትን የሌላ አዳዲስ  መስሪያቤት ሰራተኞች መልካቸውን ሳይቀር የማያውቁዋቸውን ሰዎች ግምገማ በድፍረት ይሞሉ ነበር፡፡በመሀል በተቃዋሚነት ያልተፈረጁትን እና አባል መሆን የሚፈልጉ ካሉ በምደባ እና በእድገት አያባበሉ ወደ ድርጅቱ የማግባባት ስራ ተከናወነ፡እኔ ስራየን እንጂ የፓርቲ አባል መሆን ፍላጎት የለኝም ያሉት ደግሞ ቀደም ሲል በተለያዩ የውጭ ሀገራት ሳይቀር ከፍተኛ ስልጠናዎችን ተከታትለው ስራቸውን በብቃት ሲወጡ የነበሩ በርካታ ባለሙያዎች አብዮታዊ ዲሞክራሲን ባለመቀበላቸው ብቻ  ዘራቸው እየታየ ከስራቸው ከተባረሩት መካከል ከዚህ  በታች የተዘረዘሩት ለማሳያ ያክል የቀረቡ ሲሆኑ አንድም የትግራይ ብሄር  ተወላጅ አለመባረሩን አንባቢያን ሊገነዘቡት ይገባል፡፡ሌላው እና አስገራሚው ነገር በወቅቱ  የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን እያገለለ እየተካሄደ ያለው ምደባ ያሳሰባቸው የኢህዴድ አባላት ጥያቄያቸውን ለሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ቢያቀርቡም ወ/ሮ አላማዝ ካህሳይ እያንዳንዱን ኦሮሞ እቢሮአቸው ጠርተው አርፈው እንዲቀመጡ አለዚያ እንደሚባረሩ በዛቻ ገልጸውላቸዋል፡፡በወቅቱም ከፍተኛ ተቃውሞ ያሰማው አቶ ሙሉጌታ መኮነን ያለስራ ለአንድ ዓመት ደመወዝ ብቻ እየተከፈለው ሊሰራ በማይችል ዘርፍ የቡድን መሪ ሁኖ ሲመደብ በስሩ ግን ምንም ሰው አልነበረም፡፡

ተ.ቁ            ስም     የነበራቸው ሀላፊነት

ብሄር

1 አቶ መሳይ ግርማ የጥራት እና ደረጃ መ/ቤት ዋና ዳይሬክተር

ኦሮሞ

2 አቶ ጋሻው ወርቅነህ የጥራት እና ደረጃ መ/ቤት ምክትል ዳይሬክተር

አማራ

3 አቶ ተፈራ ማሞ የኤሌክትሪክል ላብራቶር  ሃላፊ

ኦሮሞ

4 አቶ ሀይሉ የመሳሪያ ጥገኛ አገልግሎት ሃላፊ

ኦሮሞ

5 አቶ ደሬሳ ፉፋ የሰርተፊኬሽን አገልግሎት ዳይሬክተር

ኦሮሞ

6 አቶ መስፍን የስልጠና አገልግሎት ዳይሬክተር

አማራ

7 አቶ አዱኛው መስፍን የጥራት ማኔጅሜንት አሰልጣኝ

አማራ

8 አቶ እንዳ የኢንፎርሜሽን አገልግሎት ሀላፊ

አማራ

9 አቶ አመሃ በቀለ የጥራት ማኔጅሜነት አሰልጣኝ

አማራ

10 አቶ ሂርጳ የጥራት ማኔጅሜነት አሰልጣኝ

ኦሮሞ

11 አቶ መረሳ የሰርትፊኬሽን ኤክስፐርት

ኦሮሞ

12 አቶ ቴወድሮስ ዘካሪያስ የፍተሻ ላብራቶር ኤክስፐርት

አማራ

13 አቶ  ልኡል የባህርዳር ቅርንጫፍ  ሀላፊ

አማራ

14 የሰርትፊኬሽን ሲስተም ኦዲተር የነበሩት

ኦሮሞ

15 የድሬደዋ ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩት አማራ
16 የናዝሬት ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩት ኦሮሞ
17 የሀዋሳ  ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩት ደቡብ

ታማኝ የህወአት አባላት  በባትሪ  ከሌላ ቦታ ተፈልገው ያለ ልምድ  እና ችሌታቸው  በከፍተኛ አመራርነት ሲመደቡ የተለሳለሰ አቋም ያላቸውን እና የአባልነት ጥያቄ ሲቀርብላቸው ጥያቄውን የተቀበሉ ነባር የመስሪያቤቱ ሰራተኞች የፍርፍሪው  ተቋዳሽ ሁነዋል፡፡በዚህ ምደባ እስከቡድን መሪ ያለው ሀላፊነት ያለ ፓርቲ አባልነት ወይም ያለ ትግራይ ተወላጅነት በምንም መልኩ ለተራው ሰራተኛ አይሰጥም፡፡

ተ.ቁ  ስም   ቀደም የነበራቸው ሀላፊነት አሁን የተሰጣቸው ሀላፊነት ብሄር
1 ወ/ሮ አልማዝ ካህሳየ የኢንስፔክሽን አገልግሎት ዳይሬክተር የደረዳዎች ዋና ዳይሬክተር ትግሬ
2 አቶ ወንዶሰን ፍስሃ የካሊብሬሽን አገልግሎት ሀላፊ  የሜትሮሎጂ ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ትግሬ
3 አቶ አርአያ መከላከያ ኢንጅነሪንግ የአክረዲቴሽን ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ትግሬ
4 አቶ ጋሻው ተስፋዬ የፍተሻ ላብራቶር ኤክስፐርት የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ትግሬ
አቶ ገብሬ ኝግድ እና ኢንዱስትሪ ኤክስፐርት በደረጃዎች ኢጀንሲ ዳይሬክተር ትግሬ
6 አቶ ብርሀኑ ተካ ረዳ የፋይንነስ አስተዳደር ዳይሬክተር የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የፋይናንስ ዳይሬክተር ጉራጌ
7 ወ/ሮ ገነት ገ/መድህን የፍተሻ እና ካሊብሬሽን  አገልግሎት ዳይሬክተር የአክረዲቴሽን ጽ/ቤት ዳይሬክተር ትግሬ
8 ወ/ሮ ብርሀን ብሂል የአዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጸሀፊ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሰው ሀብት እስተዳደር ሀላፊ ትግሬ
9 አቶ ብርሀኑ ተካ የሰርቪስ ሹፌር የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የተራንስፖርት መምሪያ ሀላፊ ትግሬ
10 አቶ ተክኤ ብርሀኔ የኮሙኒክሽን ሰራተኛ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ትግሬ
11 አቶ ዳዊት  የሰርቪስ ሹፌር የሜትሮሎጂ ኢንስቲቲዩት የትራንትፖርትመምሪያ ሀላፊ ትግሬ
12 አቶ ጸጋዬ ኢንስፔክተር የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ሀላፊ ትግሬ
13 አቶ ዘነበ ኢንስፔክተር የገበያ ጥናት ሀላፊ ትግሬ

ቀደም ሲል እንደማናኛውም ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳሉ የመንግስት መስሪያቤቶች የሚታዩ ችግሮች ቢኖሩም የተወሰደው እርምጃ ግን የወቅቱን የትግሬዎች የንግድ እንቅስቃሴ ያላንዳች ተቆጣጣሪ እንደፈለጉት ለማሽከርከር ታስቦ አንደሆነ ይታወቃል፡፡ለዚህም መነሻ የሚሆነው በተለያዩ ጊዜያት በቆርቆሮ፣በብረታብረት፣በማዳበሪያ፣በሳሙና፣በከብሪት፣በሲሚንቶ ፣በዘይት፤በጨርቃ ጨርቅ ፣ በባትሪ ድንጋይ፣በኤሌክትሪክ ገመዶች የመሳሰሉት ምርቶች ላይ ተደጋጋሚ ችግር ተከስቶ በበላይ አካል የስልክ ትእዛዝ ደረጃቸውን ያልጠበቁ ምርቶች ለህብረተሰቡ እንዲሰራጩ ተደርጉዋል፡፡ለአብነት ያክል የአቢሲኒያ ሲሚንቶ ፋብሪካ በጥራት ጉድለት ምክንያት እንዳያመርት አገዳ መስሪያቤቱ ሲያስተላልፍ በወቅቱ የከተማ ሚኒስትር የነበሩት ዶ/ር ካሱ ኢላላ  ፍተሻውን ያከናወኑ ባለሙያዎችን በግላቸው ቢሮ ድረስ በማስጠራት ትክክል አደላችሁም፤ልማታችንን እያደናቀፋችሁ ነው፤ኢንቬስተሮች ወደ ሀገራችን እየመጡ እንዳይሰሩ መሰናክል እየፈጠራችሁ ስለሆነ አቁሙ ሲባሉ የመስሪያቤቱ ሀላፊዎች እገዳውን ባስቸኩዋይ አንዲያነሱ ቀጭን ትእዛዝ አስተላለፈዋል፡፡መስሪያቤቱም እንዲፈርስ የተደረገው ባለሞያዎችም የተፈናቀሉት ሆን ተብሎ ያለ አግባብ  መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲረዳው ያስፈልጋል፡፡

↧

በስዊድን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ላልተወሰነ ጊዜ ተዘጋ

$
0
0

ስዊዲን
(ዘ-ሐበሻ) “ባለፉት ወራት በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ክርስቲያናዊ ያልሆኑ ሥነምግባራቶች በመከሰታቸውና ያለመግባባት በመፈጠሩ፤ ይህን ተከትሎ በማህበረ ምህመናኑ (አባቶች፣ እናቶች፣ ወንድሞች፣ እህቶችና ህፃናት ላይ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ግምት ውስጥ በማስገባት ከነገ ታህሳስ 13 ቀን 2013 (December 21,2013) ጀምሮ መንፈሳዊ አገልግሎቱን ለጊዜው እንድናቋርጥ ተገደናል” ይላል በስዊድን ስቶክሆልም ከተማ ውስጥ የሚገኘው የመንበረ ጸባዖት ቅድስ ሥላሴ ቤ/ክ ደጃፍ ላይ የተለጠፈው ማስታወቂያ።

የዘ-ሐበሻ የስዊድን ዘጋቢ ባስተላለፈው መረጃ መሠረት ቀድሞ ገለልተኛ ሆኖ የተመሠረተው ይህ ቤተክርስቲያን በአንዳንድ መዘምራን እና የማህበረቅዱሳን አባላት አማካኝነት በተነሳ ጥያቄ የዛሬ ሁለት ዓመት የአቡነ ጳውሎስ ስም በቅዳሴ ላይ እየተጠራ ግን በገለልተኛነቱ እንዲቆይ ተወስኖ አቡነ ጳውሎስ ካረፉ በኋላም የ6ኛው ፓትሪያሪክ አቡነ ማቲያስ ስም እየተጠራ በገለልተኛነት ቆይቶ ነበር። እንደ መረጃ ምንጫችን ገለጻ ከ2 ወራት በፊት እንደገና፤ በቤተክርስቲያኑ አንዳንድ መዘምራን እና የማህበረ ቅዱሳን አባላት ባነሱት ጥያቄ ቤተክርስቲያኑን ወደ ኢትዮጵያው ሲኖዶስ ስር ለማስገባት እንስቃሴ ተጀምሮ አሁን ያለው የቤተክርስቲያኑ ቦርድ በአዳዲስ ሰዎች እንዲተካ፣ የሰበካ ጉባኤውም አስተዳደር በአዲስ መልክ እንዲዋቀር፤ እንዲሁም ቤተክርስቲያኒቱ በካህናቱ እንድትመራ ጥያቄ አቅርበዋል።

በእንደዚህ ያለ ሁኔታ ውስጥ ያለው የስቶክሆልሙ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ ከገለልተኛነት ወደ ኢትዮጵያው ሲኖዶስ ለማስገባት ውሳኔ እንዲሰጥ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ባለበት በዚህ ወቅት ይህን ተከትሎም በቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ቦርዱ በመግለጫው ላይ እንዳለው ክርስቲያናዊ ያልሆኑ ሥነምግባራቶች መከሰትና ያለመግባባትም መፈጠር ጀምሯል።

የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳደር ቦርድ እና ሰበካ ጉባኤው ይህን አለመግባባት ለማብረድ ቤተክርስቲያኑን ላልተወሰነ ጊዜ መዝጋቱን ያሳወቀ ሲሆን “ወደፊት ያለውን ሂደት ለማህበረ ምዕምናን እና ምዕመናቱ እናሳውቃለን” ብሏል።

↧

በኮራ የሙዚቃ አዋርድ ሃገራችንን ያስጠራችው ድምፃዊት ሚካያ በኃይሉ አረፈች

$
0
0

mikaya (ዘ-ሐበሻ) “ሸማመተው” በሚለው የሙዚቃ አልበሟ ባሳየችው ብቃት በተለይም በቀጣይነት በኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ላይ ነብስ ሊዘሩበት ይችላሉ የሚል ግምት ከሚሰጣቸው አርቲስቶች ውስጥ ገብታ የነበረችው ድምፃዊት ሚካያ በኃይሉ በ37 ዓመቷ ከዚህ ዓለም ተለየች። የቀብር ሥነስርዓቷም ዛሬ በለብይ መካነ መቃብር መፈጸሙን ከአዲስ አበባ የመጡ መረጃዎች አመልክተዋል።

ላለፉት 3 ሳምንታት ያህል ለጊዜው ምንነቱ ባልተገለጸ ሕመም ስትሰቃይ እንደነበር የደረሰን መረጃ አመልክቶ ትናንት ማምሻውን ግን ህመሙ አላላውስ ሲላት ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በቤተሰቦቿ አማካኝነት ብትወሰድም ሕይወቷ ሊተርፍ እንዳልቻለ ተገልጿል።

አንድ ሙሉ የሙዚቃ አልበም እንዲሁም ነጠላ ዜማዎችን በመልቀቅ ታዋቂነትን ያተረፈችው ሚካያ ትምህርቷን የተከታተለቸው በቤተልሔም አንደኛ ደረጃ እና በአብዮት ቅርስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ እንዲሁም የመጀመሪያ ዲግሪዋን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝታ ሁለተኛዋን ዲግሪ ለመጨረስ ጥቂት በቀራት ሰዓት ሞት እንደቀደማት በሕይወት ታሪኳ ላይ ተቀምጧል።

ድምጻዊት ሚካያ በኃይሉ በአፍሪካ ኮራ የሙዚቃ አዋርድ ላይ ተሳትፋ፤ በተሳተፈችበት ምድብ በ2010 ዓ.ም ከምርጥ 20 ድምፃውያን መካከል አንዷ ሆና በመመረጥ እስከ ውድድሩ ግማሽ ፍጻሜ ድረስ ደርሳ እንደነበር ይታወሳል።

የአንዲት ሴት ልጅ እናት የሆነችው ድምጻዊት ሚካያ ወዳጅ ዘመዶቿ በተገኙበት ዛሬ በለቡ መካነ መቃብር፤ የቀብር ሥነ ስር ዓቷ ተፈጽሟል። ዘ-ሐበሻ በድምፃዊቷ ሞት የተሰማውን ሐዘን ትገልጻለች።

↧
↧

በአረና መጠናከር የሰጉት ህወሓቶች ‘ዕርቅ’ፈፀሙ

$
0
0

አብረሃ ደስታ ከመቀሌ

ህወሓቶች ለሁለት ተከፍሎው የደብረፅዮን (የአዲስ አበባ) ና የአባይ ወልዱ (የትግራይ) ቡድን ተሰይመው ሲነታረኩ መቆየታቸው ይታወቃል። ከወራት በፊት ጀምሮ ደግሞ ሁለቱም ቡድኖች ‘ለማስታረቅ’ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ጠቅሼ ነበር።

ትንቅንቅ

ትንቅንቅ

አሁን አቶ ስብሃት ነጋ (ከቢተው በላይ ጋር በመሆን) ሁለቱም ባላንጣ ቡድኖች ‘ማስታረቅ’ ችለዋል። ዕርቁ የተፈፀመው በነ ደብረፅዮን ቡድን አሸናፊነት ነው። የነ አባይ ወልዱ ቡድን በመሸነፉ ምክንያት አቶ አባይ ወልዱ ከነ ስብሃት ነጋ ጋር እንዲስማማ ምክንያት ሁነዋል። የነ አባይ ቡድን የተዳከመበት ምክንያት ለሁለት በመከፈሉ ነው። አቶ አባይ ወልዱ ከአቶ ቴድሮስ ሐጎስ፣ ኢያሱ ተስፋይ፣ ተክለወይኒ አሰፋ፣ ኪሮስ ቢተው፣ በየነ መክሩ ወዘተ መግባባት ባለመቻሉ ከአዲስ አበባዎቹ ጋር ለመስማማት ተገደዋል።

tewedrosበስምምነቱ መሰረት ህወሓት በአዲስ አበባዎቹ ፕላን ይጓዛል። በ’መለስ ራእይ’ ስም ህዝብ መጀንጀን ይቀራል። በሙስና ሰበብ ባለስልጣናት ማሳሰርም ይቀራል። ከአሁኑ በኋል ከፍተኛ የህወሓት ባለስልጣናት በሙስና ሰበብ አይታሰሩም። በቀጣዩ የኢህአዴግ ጉባኤ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር ከህወሓት እንዲሆን ጥረት ይደረጋል (ዶር ቴድሮስ አድሐኖም)።

ይህ የህወሓቶች የ’ዕርቅ ሂደት’ ባብዛኛው የብአዴን አመራር አባላትና በተወሰኑ የኦህዴድ መሪዎች ቅሬታ አስነስተዋል። ህወሓቶች ለመታረቅ የተገደዱበት ምክንያት በተቃዋሚዎች ስልጣን እንዳይነጠቁ በመስጋት ነው። ዓረና ፓርቲ ለህወሓቶች ትልቅ ስጋት በመፍጠሩ ነው። የፀጥታ ሃይሉ መፈራረስም ሌላ ህወሓቶች ያስደነገጠ ጉዳይ ነው። በዕርቁ ሂደት ከፍተኛ ሚና የተጫወተው አቶ ስብሃት ነጋ ነው።

የዕርቅ ሂደቱ በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ከፍተኛ አለመግባባት ሊፈጥር ይችላል። ኢህአዴግ በዉስጥ ለውስጥ የስልጣን ሹክቻ ምክንያት የሚዳከምበት አጋጣሚ መፈጠሩ አይቀርም። ዕርቁ ግዝያዊና ስትራተጂካዊ ብቻ ነው። የታረቁት መግባባት ስለ ፈጠሩ ሳይሆን የጋራ ጠላትን ለመከላከል ብቻ ነው።

↧

ኢኮኖሚያችን ሲያድግ የህዝቡ ኑሮ ለምን አሽቆለቆለ?

$
0
0

Question-Markላለፉት 8 እና ዘጠኝ ዓመታት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሁለት አሃዝ አያደገ ነው ሲባል እንሰማለን፤  የእድገት ፍጥነቱ  ላይ የሚነሱ በርካታ ጥያቄውች  ቢኖሩም መንግስት  የመንገድ ግንባታ ፣ የኃይል ማመንጫ ግንባታወችን እና መሰል ነገሮችን  በመጥቀስ እድገት እንዳለ አስረግጦ ይከራከራል::  በሌላ በኩል የኢኮኖሚ እድገቱ ተመዘገበ በሚባልባቸው ዓመታት በዋጋ ንረት የህዝቡ ኑሮ ከጊዜ ወደጊዜ እያሽቆለቆለ  እንደሆነ በግልፅ የሚታይ ነገር ነው:: ታዲያ  የኢኮኖሚ እድገት አለ በተባለባቸው ዓመታት የህዝቡ ኑሮ ለምን አሽቆለቆለ? ይህን ጥያቄ ከ 7 ዓመት በፊት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ  ተጠይቀው የሰጡት መልስ የዋጋ ንረቱን የኢኮኖሚ እድገቱ እራሱ የፈጠረው ጉዳይ ነው ነገር ግን ቀስ በቀስ እድገቱ ሲቀጥል ራሱ እድገቱ ችግሩን ይፈታዋል ብለው ነበር፤ ነገር ግን ከሰባት ዓመት በዃላም እንኩአን ሊሻሻል  የህዝቡ የኑሮ ሁኔታ ከቀን ወደቀን እየባሰበት ሂዷል::  ችግሩ የተለያዩ  ምንጮች ቢኖሩትም በዋናነት በ 2 ከፍሎ ማየት ይቻላል::

፩. የኢኮኖሚ እድገቱ ምንጭ

፪. የሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር

የኢኮኖሚ እድገት ማለት በአጭሩ ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ተጨማሪ ሀብት መፍጠር ማለት ነው::  በመጀምሪያ ላለፉት 8  እና ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ ዉስጥ  የተፈጠሩት ተጨማሪ ሀብቶች ምንድን ናቸው ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል ፤  በአብዛኛዉ ሀገሪቱ ዉስጥ የተፈጠሩት ሀብቶች ከመንገድ ፣ ከሕንፃ እና ከ ከኃይል ማመንጫ ከግንባታ ጋር የተያያዙ ናቸው:: በመቀጠልም የዚህ ሀብት የገንዝብ ምንጭ ምንድን ነው ብሎ ማየት ያስፈልጋል፤ የገንዘቡ ምንጭ በዋናነት ከብድር እና እርዳታ የተገኘ ሀብት ነው ፣ በተለይም በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ 1998 ዓም ጀምሮ በሶማሊያ በመጀመሪያ የእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት በመቀጠልም የአልሻባብ እንቅስቃሴ መጠናከር ለኢትዮጵያ ትልቅ ሲሳይ ይዞ ነው የመጣው:: በሶማሊያ ያለዉን ሁኔታ  ለመቆጣጠር ምዕራባዉያኑ የሚያደርጉትን ጥረት በመደገፍ  በዋና አጋርነት የተሰለፈችዉ ኢትዮጵያ ላለፉት ስምንት ዓመታት በየዓመቱ በቢልየን ዶላር የሚቆጠር ገንዘብ በእርዳታ መልክ ከምዕራብ ሃገራት እንድታገኝ አድርጓታል:: ይህም ማለት ሀገሪቱ ዉስጥ የጎላ  የኢኮኖሚያዊ መዋቅር ፣ የአሰራር ስርዓት  እና የቴክኖሎጅ ለውጥ ሳይኖር ከፍተኛ ገንዘብ ወደኢኮኖሚው ፈሰስ እንዲሆን አድርጓል:: በሌላ አገላለፅ  የቆየው የሀገሪቱ  ኢኮኖሚ የጎላ የምርት ጭማሪ ሳይኖረው ከዉጭ የተገኘ ብድር እና እርዳታ ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ተጨመረ እና የኢኮኖሚዉ መጠን አደገ ማለት ነው::  ስለዚህ የህዝቡን የኑሮ ሁኔታ እና የሀገሪቱን ተወዳዳሪነት ሊያሻሽል የሚችል የግብርና እና የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ የጎላ  ለዉጥ ሳይታይ ለመሠረት ልማት ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ፈሰስ የተደረገው ገንዝብ የገንዘብ አቅርቦትን (Money Supply) በመጨመር እና  የአገልግሎት ዘርፉ ( Service sector) ከሌሎቹ የኢኮኖሚ ዘርፎች ተነጥሎ እንዲለጠጥ እንዲሁም ዋጋ እንዲንር በማድረግ አብዛኛዉን ሕዝብ ለችግር አጋለጠ ::

ከብድር እና እርዳታ የተገኘው ገንዘብ መሰረተ ልማት ላይ ሲዉል ከላይ የተገለፀው ችግር ቢኖርበትም በአንፃሩ የመሰረተ ልማት መስፋፋት የማምረቻ ወጭ ( cost of production) እንዲቀንስ በማድረግ የሚያስገኘው ጥቅም አለ ፤ በተጨማሪም ገንዘብ ገንዘብን ይፈጥራል “ money creats money” በሚለው የኢኮኖምክስ  መርህ መሰረት ኢኮኖሚዉ ዉስጥ የተረጨው ገንዘብ በአብዛኛዉ አገልግሎት ዘርፉ ላይ የፈጠረው ተጨማሪ ሀብት አለ:: ነገር ግን ይህ የተፈጠረ ተጨማሪ ሀብት በጠንካራ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር ስላልተመራ ወደጥቂት ሰወች እጅ እንዲገባ ሁኗል::  ሃብቱ እጃቸው የገባ ሰወችም የኢኮኖሚዉን መዋቅር ሊለዉጡ የሚችሉ እንደኢንዱስትሪ አይነት ዘርፎች ላይ ከመሰማራት ይልቅ ከሙሰኛ ባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለዉን የከተማ ቦታ በኢንቨስትመንት እና በሊዝ ስም በመዉሰድ ህንፃ በመገንባት እየተለጠጠ ላለው የአገልግሎት ዘርፍ በማከራየት በአቁአራጭ ከፍተኛ ገቢ ለመሰብሰብ ተጠቀሙበት::

በሌላ በኩል የሀገሪቱ የመሬት አስተዳደር ስርዓት በሙስና የተጨማለቀ እና ወጥ ስላሆነና አዳዲስ ብቅ ለሚሉ ባለሀብቶች መሬት ማግኘት ከባድ ስለሆነ ሀገሪቱ አሁን ባለችበት ተጨባጭ ሁኔታ ወሳኝ ሀብት (strategic resource) የሆነዉን የከተማ ቦታ ቀድመው የያዙ ባለሀብቶች የገቢያ ዉድድሩን ሚዛናዊ እንዳይሆን በማድረግ አዲስ የሚፈጠሩ ተወዳዳሪያቸውን በቀላሉ ከገቢያ ያስወጣሉ:: በተጨማሪም እንደነዚህ አይነቶቹ  ባለሀብቶች በአብዛኛው የፖለቲካዉ እና የግዥዉ ፓርቲ ጥገኛ ስለሆኑ የሚጠበቅባቸዉን ያክል  ግብር እና ታክስ አይከፍሉም:: ሥራቸዉን ስለሚያውቁም በሀገሪቱ በረጅም ጊዜ ሊከሰት ይችላል ብለው የሚፈሩትን ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ስለሚሰጉ የሚያገኙትን ትርፍ ወደዉጭ ያሽሻሉ ፤ በጎን ሙሰኛ ባለስልጣናትም የሚዘርፉትን ገንዘብ ከሀገር ያሸሻሉ:: ከዚህ ላይ ፋይናንሽያል ትራንስፓረንሲ ኳሊሽን  ያወጣዉንና ኢትዮጵያ በህገወጥ የገንዘብ ፍሰት (illicit financial flow) በፈረንጆቹ ከ 2000 እስከ 2009 ያጣችዉን 11. 7 ቢልየን ዶላር ልብ ይሏል::

ለማጠቃለል የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ጤናማ ሁኖ እንዲያድግ ከተፈለገ ከላይ የተጠቀሱት  የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ መዋቅር ድክመቶች መስተካከል የሚገባቸዉ ሲሆን ፤ በዉጭ ብድር እና እርዳታ ላይ መንጠልጠሉን ቀንሶ ከሀገር ቤት በፍትሃዊነት ከሚሰበሰብ ግብር ሊሆን ይገባል:: ከዉጭ የሚገኘዉን ሀብትም  በብዛት መሰረተ ልማት ላይ ብቻ ማዋሉ የሚያስከትለዉን ችግር ጥልቅ ጥናት በማካሄድ  መመርመር እና  ገንዘቡ ከመሰረተ ልማቱ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪው እና የእርሻዉን ዘርፍ መዋቅር ወደተሻለ ደረጃ እንዲደርስ ለማስቻልም መሰራት አለበት:: ከሁሉም በላይ ግን የኢኮኖሚ ነቀርሳ የሆነዉን ሙስና ለማስወገድ ከአንድ ፓርቲ የበላይነት ወደ መድብለ ፓርቲ ስርዓት መሸጋገር እንዲሁም ተጠያቂነትን ሊያጠናክሩ የሚችሉ እንደገለልተኛ ፍርድ ቤቶች ፣ የግል መገናኛ ብዙሃን  የመሳሰሉትን ተቋማት መፍጠር ያስፈልጋል:: ይህ ካልሆነ ግን ሀገሪቱ ሽህ ጊዜ ብታድግ የኢኮኖሚውን ፍሬ ጥቂቶች እየበሉ የአብዛኛዉ ሕዝብ  ኑሮ ማሽቆልቆሉ ይቀጥላል::

 

 

 

↧

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከዩኒቨርስቲ ተባረሩ

$
0
0

ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ እንደዘገበው፦ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲና የጤና ነክ ተማሪዎች ለውዝግብ የተዳረጉት በሚሰጠው ድግሪ ሲያሜ እንደሆነ ከቦታው የደረሰን ማስረጃ ያስረዳል፡፡ ከ1ኛ እስከ 4ተኛ ዓመት ያሉ ተማሪዎች ሲመደቡ ዲግሪያቸው የጤና ሳይንስ መኮንን (Public Health Officer) እንደሚባል እንደተነገራቸው ገልፀው ነገር ግን ዩኒቨርሲቲው አሁን የህብረተሰብ ጤና (Public Health) ብቻ የሚል ስያሜ እንደሰጣቸው ተናግረዋል፡፡ ተማሪዎቹ ጉዳዩን በማሳወቅ ማብራሪያ የጠየቁ ሲሆን “‹የህብረተሰብ ጤና አጠባበቅ› የሚለው እናንተን አይመጥንም” እንደተባሉ ገልጸዋል፡፡
Debre_Markos
በመልሱ ያልረኩት የዲፓርትመንቱ ተማሪዎች ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ከህዳር 28 ጀምሮ ደረጃውን ጠብቀው ለሚመለከተው የዩኒቨርስቲው ኃላፊዎችና ለፕሬዚደንቱ ጥያቄ ቢያቀርቡም “ብትማሩ ተማሩ ባትማሩ ግቢውን ለቃችሁ ትወጣላችሁ” የሚል ማስፈራሪያ እንደተሰነዘረባቸው አሳውቀዋል፡፡ ታህሣስ 05 ቀን 2006 ዓ.ም የተሰበሰበው የዩኒቨርስቲው ሴኔት 173 ተማሪዎች ከግቢ እንዲባረሩ ወስኗል፡፡

ከሰኞ ታህሣስ 7 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ መታወቂያቸውን በፖሊስ ተቀምተው ከግቢው እንዲባረሩ የተደረጉት 173 ተማሪዎች በአሁኑ ሰዓት ሜዳ ላይ ተበትነው እንደሚገኙና ለከፍተኛ ችግር እንደተጋለጡ በምሬት ተናግረዋል፡፡
ጉዳዩን ለማረጋገጥ የጤና ዲፓርትመንት ኃላፊ ወደ ሆኑት አቶ ዱቤ ጃራ ስልክ ደውለን የተባለው ነገር መከሰቱን ጠቅሰው ነገር ግን “ውሳኔው በአግባቡ ነው የተላለፈው፤ ይህ ስያሜ ከ1954 ዓ.ም ጀምሮ የነበረ ነው፤ ካሪኩለሙ ላይ ያለው የህብረተሰብ ጤና (Public Health) እንጂ የህብረተሰብ ጤና መኮንን (Public Health Officer) አይደለም” ብለዋል፡፡

አቶ ዱቤ በተደጋጋሚ የዲግሪው ስያሜ “አዲስ የተሰጠ ስያሜ አይደለም” ካሉ በኋላ በተጨማሪም “ተማሪዎቹ ያለ ትምህርት ለ11 ቀናት ግቢ ውስጥ መቀመጣቸው ተገቢ ስላልሆነ ከግቢ እንዲወጡ ተደርጓል” ብለዋል፡፡ በተያያዘ ጉዳይ ከጊቢው የተባረሩ ተማሪዎች ከፍተኛ ችግር ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ስሙ እንዲገለፅ ያልፈቀደ አንድ ተማሪ “መጠለያ፣ ልብስና ምግብ” እጅግ እንደቸገራቸው ገልፆ በተለይ ሴት ተማሪዎቹ መጠለያ እንዲሰጣቸው ለምስራቅ ጎጃም ዞን የሴቶች ጉዳይ ቢያመለክቱም “ዩኒቨርሲቲው ያባረራቸውን ብንረዳ እንጠየቃለን፤ ስለዚህ ልንረዳቸው አንችልም ማለታቸው ታውቋል፡

↧

ሰበር ዜና ከሳውዲ አረቢያ ! ሮብ ምሽት በመንፈሃ ዙሪያ መጠነ ሰፊ ጥብቅ ፍተሻ ተጀመረ !

$
0
0

ነቢዩ ሲራክ

* በሪያድ የኢትዮጵያ ኢንባሲ የተጀመረውን ፍተሻ በማረጋገጥ ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው ዜጎች በሰላማዊ መንገድ በአስቸኳይ ለጸጥታ አስከባሪዎች እጅ በመስጠት ወደ መጠለያ በመግባት ወደ ሃገር እንዲገቡ ማምሻውን ባወጣው ማስታወቂያ አሳስቧል ። ካለፉት ሳምንታት ወዲህ በሪያድ መንፉሃ በኢንባሲውና በሃገር ሽማግሌዎች የተቋቋሙ የመረጋጋት ኮሚቴ አባላት ወደ መንፉሃና ኢትዮጵያውያን በሚበዙባቸው ምንደሮች በመንቀሳቀስ ዜጎች ያለ ምንም ጉዳት እጃቸውን ሰጥተው ወደ ሃገር ለመግባት እንዲዘጋጁ የመከረ ቢሆንም ጥረቱ አልተሳካም ነበር ።  የሪያድ ኢናባሲ የሽማግሌዎች ኮሚቴ አባላት ባደረጉት ቅስቀሳ ወደ ሃገር ለመግባት ባልተጨበጠ ተስፋ የተዘናጉ ህጋዊ መኖሪያ ፈቃድ ያልያዙ ወደ ሃገር በመግባቱ ላይ እንዳያቅማሙ መምከራቸው ይጠቀሳል !

* አሁን በተጀመረው የመንፉሃ ፍተሻ ማዋከብ የለበትም ። ህጋዊ መኖርያ ፍቃድ የሌለውን ብቻ እንደሚይዙና ከአሰሪው (ከከፊሉ) ጋር ይሰራል አይሰራም የሚባል ማጣራትም ሲካሔድ አልተስተዋለም ተብሏል ።

* ከአሰሪው ጋር የማይሰራ እንደ ህገ ወጥ እንደሚቆጠር የሳውዲ ህግ በግልጽ ያሳወቀ ሲሆን የጅዳና የሪያድ ኢንባሲ ይህ ህግ እንደሚጸና ተደጋጋሚ ማስታወቂያ በማውጣት “በሰላም ወደ ሃገራችሁ ግቡ!” በማለት ሲመክሩና ሲወተውቱ ሰንብተዋል።

* በቀጣዩ መጠነ ሰፊ የማጣራት ዘመቻም ከአሰሪው (ከከፊሉ) ጋር የማይሰራ እንደ ህጋዊ ስለሚቆጠር የሳውዲ መንግስት በፈቃደኝነት እጃቸውን የሚሰጡት ወገኖች ወደ ሃገር መስደድ እንደተጠናቀቀ አንወጣም ባሉት ላይ ፍተሻ በማድረግ በእስራትና በገንዘብ እንደሚቀጣ በኢንባሲና በቆንስል መስሪያ ቤቶች በኩል ባስተላለፈው ማስጠንቀቂያ አስታውቋል ።

*  ቁጥራቸው በሽዎች የሚገመቱ ዜጎች እስካሁንም ድረስ ወደ ሃገር ግቡ የሚለውን ጥሪ ባለመቀበል የተዘናጉበት ሁኔታ ይስተዋላል ። ይሁን እንጅ ካለፉት ሁለት ቀናት ወዲህ መንቀሳቀስ  ያልጀመረው የጅዳ አካባቢ በርካታ ነዋሪዎች ወደ ሃገር ቤት ለመግባት ወደ ተዘጋጀው መጠለያ በመግባት ላይ ናቸው ። ከአሰሪያቸው ጋር ስለማይሰሩ ህገ ወጥ የተባሉት ግን አሁንም እንቅስቃሴ አለማሳየታቸው ይመለከታል ።

* የጅዳ ቆንስልና የወገን ለወገን ደራሽ ኮሚቴውም አውቶቡስን በአፋጣኝ እንዲቀርብ በማድረጉ ረገድ ከቆንሰሉ ሃላፊዎች ጋር በመተባበር ለነዋሪው ድጋፍ በማድረግ ላይ ናቸው ። ህጋዊ ሰነድ የሌላችሁ አስፈላጊውን ውሳኔ መውሰድና በእድሉ መጠቀም ይጠበቅችኋል። እድሉን መጠቀም መቻል ብልህነት ነው !

554190_613712818703643_1441333089_n

ጀሮ ያለው ይስማ

ነቢዩ ሲራክ

↧
↧

የለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ጉዳይ ለወያኔ እጅ መስጠት ወይም ነጻ የመዉጣት ትግል ነዉ፤ ምዕመናን በድምጽ የማሸነፍ ሙሉ መብት አላቸዉ

$
0
0

ከአጥቃዉ ቦጋለ

የለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ጉዳይ ለወያኔ እጅ መስጠት ወይም ነጻ የመዉጣት ትግል ነዉ። ምዕመናን በድምጽ የማሸነፍ  ሙሉ መብት አላቸዉ። በድምጽ ያሸነፈ ብቻ ይረከባል፦ይህ መብት የእንግሊዝ አገር ዲሞክራሲ  ነዉና፤ ግን ሰዉ ያልዘራዉን ማጨድ አይችልም።

londonየለንደን የደብረ ጽዮን ቅድስት ማሪያም በሁለቱም ጎን ከወያኔ ጋር እከከን ልከክህ እያሉ የዉጩን ህጋይዊ ሲኖዶስ ሙሉ በሙሉ በመርሳት ብሎም ለማዳከም በቃወም  በርከት ያሉት ዉስጥ ዉስጡን የወያኔ የልማት አጋር ሁነዉ የቆዩ ናቸዉ። አንዱ ለተፈጠረዉ ችግር ምክንያት ይህ ሳይሆን አይቀርም። ወያኔ የሚሰራዉን ግፍ ጥቂት ምዕመናን ከተቃዋሚዉ ጎን ያሉ አባላት ቢያወግዙም  በልማት አጋሮች  አስተባባሪነት አብዛናወቹ ህዝበ ክርስቲያን  ወያኔ የሚሰራዉን ግፍ ጀሮ ዳባ ልበስ ብሎ ቆይተዋል።አሁን በአንድነት የቆሙት አባላት እንኳ ቀኖና ተጥሶ በመሳሪያ አፈሙዝ ግፍ የተፈጸመባቸዉን ስደተኛ የኦርቶዶክስ አባት በጽሁፋቸዉ እንኳ ማንሳት አይፈልጉም፤ ይህ የትቢት ይሁን የጎጥ ወይም የሃይማኖት ልዩነት ግልጽ አይደለም፤ ግፍን ከማዉገዝ ገለልተኛ የሆነ ትዉልድ የለምና። ወያኔም ይህ የደለላቸዉን ብዙ የወዳጆቹን  አቋም  በገንዘብ በዉስጥ መሰሪ ካድሬወችን አሰማራ ፤የልማት ተዋናኞችም ደስተኛ ሆኖ፤ አሁን ግን ደረቅ ችሆት ይጮሃሉ። ዛሬም የወያኔ የድብቅ ነጋዴዎች  መንታ መንግድ ላይ መሆናቸዉ ጥርጥር የለዉም፤ ስለወያኔ ወንጀለኛነት በአንድ ድምጽ ሲያወግዙ አይሰማም፤ የሚሰድቡ ካድሬዉን ካህን ብቻ ነዉ፣ አህያዉን ፈርቶ ዳዉላዉን ይላሉ ይህ ነዉና። ይልቅስ አባላት ጸረ ወያኔ አቋም ይዘዉ ወንጀለኛ መንግስት ከቤተ ክርስቲያናችን እጁን  ያንሳ ማለት መቻል አለባቸዉ። የተሰደዱ አባቶች የወያኔን በደል እንዲመሰክሩ ከምዕመናኑ ፊት ባይርቁ ጥሩ ነዉ።። ወያኔ ነብስ አጥፊና  የሃይማኖት አባቶችን አሳዳጅ እንደሆነ በመረጃ አስረግጠዉ ካድሬወችንና ኢምባሲዉን ያዉግዙ፤ ይክሰሱ።ግፉ እየተፈጸመ ያለዉ በኦርቶዶክስ የሃይማኖት ዕምነት ተከታይ ክርስቲያኖች ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ዉስጥ በሁሉም ዘርግ በዕምነት መገደል, መታሰር ለስደት መዳረግ መኖሩን በመረጃነት አቅርቡ። የአቡነ መርቆሪወስና የሌሎች አባተች ቀኖና ተጥሶ በወያኔ ግፍ  ጭካኔ የተሞላት ድርጊት ተሣደዉ መሰቃየታቸዉን ሳትሸማቀቁ በመረጃነት ጥቀሱ፤  የሃይማኖት ጉዳይ በመሀል ሰፋሪነት ፍጹም ሊሆን አይችልም። በሃይማኖት  ዋናዉ ቁም ነገሩ የቤተ ክርስቲያን ህንጻ በብዙ ሚሊዮን መገንባት  ብቻ ሳይሆን  ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከአንድ አምላክ በታች  ሁልጊዜም እራስ አላት ብሎ መጽናት እዉነተኛ መንገድ ነዉ። በተለይ የኛ ቤተ ክርስቲያን ብትሰደድም ገለልተኛ ሁና አታዉቅምl። ወደፊትም በአስቸኳይ ወያኔን ማስወግድ ገዘገየ ከተሰደዱ ህጋዊ አባቶች ጋር የጽድቅ ጉዟችን መቀጠል  የሃይማኖት ግዴታችን ነዉ።  ሌላዉ መንገድ ለእግዚአብሔሩ ቀርቶ ለአለማዊ የአንድነት ኑሮ አላመቸም፤  ይልቅስ የወያኔ ጅቦች  በቀዳዳዉ ይገባሉ በሚል ፍራቻ እርስ በእርስ እየተጠራጠርን ለፍርድ አናስቸግር። የዉስጥና የዉስጭ ሲኖዶስ እስቲታረቁ ከሆነ የምንጠብቀዉ እንደዚህ አይነት የሃይማኖት እምነት የለም። ኢትዮጵያ ያለዉ መንግስት ሃይማኖትን ተቆጣጥሮ ኢትዮጵያዉያንን እያሳደደ ከሆነ  ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስና ሌሎች አባቶች ጭምር እየተሳደዱ ነዉ። ይህንን በደልም ከመጥቀስ ወደኋላ አትበሉ፤ ግፍን በመረጃ ማቅረብ እኮ የአባ መርቆሪዮስ ደጋፊ አያሰኝምl፤ እኒህ የኦርቶዶክሳዊያን አባት  ለሁላችንም ሃያ አራት ሰዓት በመጸለይ ላይ እንደሆኑ አትዘንጉ፤ አስታዉሷቸዉ፤ ከህንጻዉ ይበልጣሉና።

አወ ለፍርድ ቤት በመጨረሻ ጉዳዩ ቢቀርብ ከኛ በበለጠ የኛን ቤተ ክርስቲያን የአስተዳደር መዋቅር ቁልጭ አድርገዉ ፍርድ ቤቶች ያዉቃልና ሌሎች ቤተ ክርስቲያናትም  ከእምነታችን አስተዳደር ዉጭ ገለልተኛ ነን እያላችሁ  የምትዝናኑ ችግሩ በራችሁን ላይ በአጭር ጊዜ ያንኳካል በእዉነት ስለ ዕዉነት አስቡበት። ለመሆኑ በአሁኑ ሰዓት አገር እየጠፋ ከምኑ ገለል እደምትሉ የሚጨበጥ ቁም  ነገር ጠፍቷል። ጉዳዩ በጽዮን  ብቻ አያበቃም፤ የሃይማኖት ቤታችን ወደ ንግድ ተቋም የመሸጋገር አደጋ እዬገጠመዉ ነዉ፤ እግዚአብሔር ወደ እዉነቱ ቦታችን ይመልሰን። ሌላዉ የዚህ ዓለም መንግስታዊ ፍርድ ቤት በህዝብ ድምጽ ያምናልና ለወያኔ ጊዚያዊ  የልማት ተጠቃሚ የሆናችሁ ወያኔን ካዱትና ድምጻችሁን ስጡ። የለደን ደብረ ጽዮን አባላት ብዙ ምሁራን እና የቤተ ክርስቲያን ሊቃዉንት እያሉበት  ግን በልማት ስምና ጎንደሬ ፓትራሪክ አቡነ መርቆሪዮስ ለመቃዉም ሲባል  የገለልተኛ ከበሮ አታድምቁ  ሲሆን የተበደለዉ ሁሉ ተባብሮ ማሸነፍ ፤ካልሆነም ገለል ከማለት በዓላማ ጸንቶ አወዳደቅን ማሳመር ተገቢ ነዉ። ወያኔም  ይህን የወላዋይ አቋም ይዘዉ መክረማቸዉን አስተዉሎ ጭራቸዉን በመያዝ  ፊታቸዉን መልሰዉ ወያኔ ገዳይ ነዉ ፤ጠላትም ነዉ ብለዉ መናገር እንዳይችሉ አደረገ። ምርጫዉ የኛ ነዉ፤ ለፍትህ ፤ ለሃይማኖት መቆም ወይስ ሁለት ባላ ላይ ለመቆም ወያኔ መንደር የተሰራዉን  ከንቱ የልማት ቤት በህልም እያዩ ወያኔ የጠለፋ ገመድ ታስሮ ባርነትን መምረጥ ፤ የቆጡን አወርድ ብሎ የ…..ማለት እንዲህ ነዉ። ሁሉም አባላት  ማለትም አብዛኛዉ ከተስማሙ መፍትሄዉ ቀላል ነዉ በአንድ ድምጽ የሚሰራዉን ግፍ ስናወግዝ ያኔ የወያኔ አደራጆች /ጠርናፊወች ጓዛቸዉን ጠቅለዉ ይሄዳሉ። በአሜሪካ ሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድሃኒአለም የሆነዉ እንደዚህ ነዉ፤ የወያኔ ጠርናፊወች በስድስት ወራት 700 አባላትን አስመዝግበዉ በድምጽ ለማሸነፍ  በጉባኤ ሲቀመጡ ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያዊነቱን ነብር ዝንጉርጉርነቱን አይቀይርምና  አብዛኛዉ አባላቱ አቋማቸዉን አንድ አድርገዉ ወያኔ በመካድ  ኢትዮጵያ ዉስጥም ሆነ በየአለማቱ ወያኔ ሲሰራ የቆየዉን የሃያ ሁለት ዓመታት ግፍ አስረግጠዉ በመንገር፤  ከወያኔ ስር የምንወድቀዉ ምን አዲስ የሃይማኖትም  ወይም የህዝብ ነጻነት ተገኘ በማለት  ከሆዳሞች በቀር አብዛኛዉ ምዕመናን በጸረ ወያኔ አቋሙ ወስዶ  መድሃኒአለምን እጅ መንሻ ከመሆን አዳነ።  የለንደን ጽዮን ምዕመናን ትኩረታችሁ በቻሪቲ ጉዳይ ብቻ አታድርጉ ከዉስጣችሁ የመሸጉትን የልማት አባዉራወች በመነጸር እዩ ፤ በደም የተጨማለቁ በመዋለ ንዋይ የሰከሩ ወያኔወች ገለልተኛነት የወያኔ መሸጋገሪያ መንግድ አድርገዉ የተጠቀሙ ካድሬዎች ከዬቤተ ክርስቲያን ተመንጥረዉ ያለ እሉኝታ መባረር አለባቸዉ። በሚኒሶታ የተሰገሰጉት ንፍቀ ወያኔወች የወደፍቲ እጣ ይህ ነዉ። አሁን  ቢወድቁም ሙቶ የመፈራገጥ የወያኔ ባህሪያቸዉ አይጠፋምና  ምዕመናኑ ጠንቅቆ ስለሚያቃቸዉ በሚቀጥለዉ ምርጫ ከሚኒሶታ መድሃኒዓለም ግቢ ጨርሶ እንደሚያስወጣቸዉ እርግጠና ነኝ። ዘረኛዉ ወያኔ በለደን አካባቢ መሽጎ የሚተበትበዉ የሴራ ገመድ በአጭር ቀን ይበጣጠሳል። ምዕመናኑ በአንድነት መቆም ብቻ ሳይሆን የችግሩ ዋና ምንጭ የሆነዉን ወያኔን በማጋለጥ l ማለትም የሚያካህደዉን የዘር ማጥፋት ወንጀል በአማራዉ፤ በኦሮሞዉ, በጋምቤላዉ፤ በአፋሩ ሁሊንም ብሔሮች በመክፋፈልና በማጋጨት በዘረፋ ላይ መሰማራቱን መላዉን ኢትዮጵያዉያን የዕምነት ነጻነት መንፈጉን በአ,ደባባይ ተናገሩ። የወያኔዉን ተላላኪ ካህን ብቻ ማዉገዙ ፋይዳ የለዉም፤ አህያዉን ፈርቶ ዳዉላዉን ነዉና፤ ወደቁንጮዉ አነጣጥሩ። የሰዉ ዘር አጥፊና የሃይማኖት አባቶቻችን በማሳደድ ላይ እንዳለ ለለንደን ህዝብና ለእንግሊዝ መንግስት  አስረዱ። የወያኔ መንግስት ተባባሪ እነማን እንደሆኑ አጋልጣችሁ ከስርዓቱ ጋር ተጠያቂ መሆናቸዉን አስተምሩ፤ ከዉስጣችሁ ገና በህዝብ መብት ጉዳይ በወያኔን ጠላትነት ጉዳይ የጠራ  አቋም ያልያዙ ያሉ ይመስለኛል፤ ሁላችሁን ማለቴ አይደለም፤ ገለልተኛ ነን፤ ብዙ ገንዘብ አዉተን ህንጻ ገንብተናል ማለት ብቻ በቂ አይመስለኝም፤ ይህ በሃይማኖት ቤት ብዙ አይስተናገድም። ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዮስ በግፍ የተሰቃዩ አባት መሆናቸዉን ጭራሹን  አትርሱ፤ ከቀኖናም ሆነ ከሃይማኖት አንጻር መሰረታችሁ መስመሩን መዉጣት የለበትም፤ አባ መርቆሪዮስን ወያኔ በመሳሪያ ማዉረዱን ታዉቃላችሁ። እናንተን ግን በልማት ስም ወያኔ ሊያዋርዳችሁ በአንድ ለአምስት ጥርነፋዉ በገለልተኛ መርሆ ገብቶ ህገ ቤተ ክርስቲያን እያፈረሰ ነዉ። በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ  መፍትሄ የሚገኘዉ  የእዉነቱን በመናገር እንጂ ንብረቱን ለመቆጣጠር የሚደረገዉ የሽቅድድም እሩጫ የአምላክ መልካም ፈቃድ አይጨመርበትም። አወ ወያኔ ባወጣዉ የጎጥ መስፈርት  አቡነ መርቆሪዮስ ጎንደር ክፍለ ሃገር የተወለዱ ናቸዉ፤ ሃቁ ግን ወያኔ ሊቀ ጳጳሱ ትግሬ ቢሆኑ  አያባራቸዉም።  ይኸዉ አሁንም ደግሞ ደጋግሞ የሚሾመዉ የትግሬ ፓትራሪክ፤ የትግሬ ጀኔራል ነዉ። በእርግጥ ይህ ስልቱ ትግሬዉን ከሌላዉ ህዝብ እያራራቀ የስልጣን ዘመኑን አስረዝሞ ለመዝረፍ ነዉ። ሃቀኛ የትግራይ ልጆች አሁንም በወያኔ እዬተገደሉ እዬተሳደዱ ነዉ፤ ዉሎ አድሮ የትግራይ ህዝብ በቃ ይላቸዋል፤ አዎ ብዙ ገንጣይ ወያኔን ታገሉት ግን አፍኖ አዳከማቸዉ፤ የዕራያ ህዝብ ዛሬ ከሞቱት በላይ ካሉት በታች ነዉ፤ የተንቤን ህዝብ ከተረሳ ዓመታት አልፈዋል። ኢትዮጵያን ቆራርሶ ወያኔ ለባዕድ አግር በመስጠት ያዋረዳት እየከነከነዉ ቆሽቱ ያረረዉ  የትግራይ ህዝብ ከመላዉ ኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ሁኖ  ወደክብሯ ለመመለስ ትግሉን ቀጥሏል። አየ ጉድ ጽሁፌን የወያኔ የዘር ጣጣ ጠልፎ ወሰደብኝና ብዙ ተናገርኩ፤ በሉ የጀመርኩትን ልጨርስ። አባ መርቆርዮስ ጎንደር ቢወለዱም እዉነተኛ ኢትዮጵያዊ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ/ክ  አባት ናቸዉ፤ በእርሳቸዉ የደረሰዉ ስቃይና መከራ እየረሳን  ማህበረ ቤተ ክርስቲያን ማጠናከር ወይም ባለቤት መሆን እግዚአብሔርም ሆነ ቀኖና አይደግፈንም። ሁላችን ሁሉን ህግ የሚጥሰዉን ወያኔን  ዘረኛ፤ ነብሰ ገዳይ፤  ዘራፊ ነዉ ብለን፤ ትግሬዉ፤ ኣማራዉ፤ ኦሮሞዉ፤ ሃድያዉ፤ ማለትም መላዉ ኢትዮጵያዊያን በዉጭ የዘረጋዉን የዘር መረብ በአንድነት መበጣጠስ አለብን። ችግሩ  በአሜሪካም እንዳንዣበበ ነዉ ። የዋሽንግተን የማሪያም  ቤተ ክርስቲያን እጣ ፈንታም  ተመሳሳይ ነዉ። እጀ እረጅሙ ወያኔ ለስላ ከመደበዉ 40MILLION ዶላር ብዙዉን ይህችን ትልቅ ካቴድራል አንቆ ለመያዝ የተጠቀመበት ነዉ። የልማት ሚሊዬነሮች በመቶ ሺህ በሚቆጠር ገንዘብ እዬደለሉ  ከካህናት ጋር እየተጋሩ ወያኔ መስመሩን  አንድ በአምስት በማደራጀት መርሆ ዘርግቶ በልማት ባላንባራሶቹ አማካይነት ዘርጥጦ ለመጣል ትልቅ ምሽግ ይዞ  60 ሚሊዮን የሚገመት  ንብረት በመጨረሻ የወያኔ ጦር ሜዳ ይሆናል። ቢያንስ በአቡነ መርቆርዮስ ማለትም በስደደተኛ አባቶች አስመዝግበዉ ቢቆዩ መልካም ነበር። ችግሩ ግን ከወያኔ ጋር በልማት የተቆራኙ ብዙ ሃብታሞች  ስላሉ  ከወያኔ ስዉር ሰንሰለት ነጻ የሚሆኑበት መንግድ እየጠበበ ሳይመጣ አይቀርም፤ በአቋራጭ እግዚአብሔር ከወያኔ እንደሚገላግለን  ግን ሙሉ ተስፋ አለኝ። ማሪያምን ከሆዳሞች ሽያጭ ያድናት። በሉ ሃይማኖታችሁንንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን መሳሪያችሁ አድርጉ፤ ስደተኛ አባቶቻችሁን አትርሱ፤ አባ መርቆርዮስም አይባርኩን፤ አባ ማትያስምም አንፈልግም እንዲያዉ ከንቱ ምክንያት አልባ ህዝቡን ኦርቶዶክሳዊ ባልሆነ መንገድ አታድክሙት። የግፍ አገዛዝ በቃ በሉ፤ በከንቱ ዳር ዳርና የገለልተኛ ማሃል ሰፋሪነት  በሃይማኖት መሪነታቸዉ ብቻ የተሰቃዩ አባቶችን ከመርሳት ደረጃ አያደርስም።  ለህዝብ መብትና ለቤ/ክ የአስተዳደር ነጻነት ታገሉ፤ የአንድነት መድሃኒታችን የጎጠኛነት መርዝን ይነቀል። እግዚአብሔር ለዕዉነትl ለፍቅር ለቆሙ ሁሉ ዘወትር አይለይምና ለሃይማኖታችሁና ለአገራችሁ ያላችሁን አቋም  ከስጋዊ ኑሮና ከባለጸጋነት  በላይ አድርጉ፤ እግዚአብሄር ሁሌ ከተበደሉ ጎን አይለይማና ሰይጣኑን ወያንን የሚያሸንፍ ሃይል ይስጣችሁ።

መልካ ገና እና የምዕራቡ ጥሩ አመት ያድርግልን

አጥቃዉ ቦጋለ

ወስብሃት ለእግዚአብሔር

↧

ቴዲ አፍሮ እና ጥሬ ጨዋዎች

$
0
0

teddy 2
ሁኔ አቢሲኒያዊ - ፒተርቦሮው ዩ.ኬ

ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) በብዙዎች ሙዚቃ አፍቃሪያን ዘንድ ትልቅ ስፍራየሚሰጠው ወጣት ከያኒ ነው፤ በሙዚቃዎቹ በሚያነሳው ሀገራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ፣ታሪካዊና ወቅታዊ ጉዳዮች የተነሳ የብዙዎችን ቀልብ ለመግዛት የቻለ ይመስለኛል፡፡ የእርሱን ታላቅነት መግለፅ የዚህ ጹሑፍ ዓላማ፣ ጥያቄም፣ የማወቅም ፍላጎት አይደለም፡፡
ይልቁንም ለዚህ አጭር መጣጥፍ መነሻ የሆነኝ ከሰሞኑ በአንዳንድ ጥቃቅን እና አነስተኛ ካድሬዎች እንዲሁም መንግስትን ለምን እንደሚቃወሙ እንኩአን በማያውቁት እንደ እነ ጃዋር መሀመድ የመሳሰሉ ሰሞንኛ ትችታቸውን በመሰንዘራቸውን ምክንያት እኔም የተሰማኝን ልጨምር በሚል ነው፡፡
እንደምናውቀው ቴዎድሮስ ካሣሁን በዚህች የሙዚቃ ህይወቱ ከዛቻ እስከመታሰር ድረስ የደረሰ መሆኑ እሙን ነው ይህም የደረሰበት የተለየ ሰው ስለሆነ ነው
ቴዲ ሺህ ዘመናት ስልጣኔያችንና ታሪካችን፣ ጥበባችን በፍቅር፣ ፍቅራችን በጥበብ የተገመደበት ውሉ ከየት ተጀምሮ የት እንደተቋረጠ ታሪክንእንጠይቅ ዘንድ እንዲህ ሲል በቅኔው ተመራምሮ ያመራምረናል፡-
ብራናው ይነበብ ተዘርግቶ ባትሮኖሱ ላይ፣
የእነ ፋሲለደስ የእነ ተዋናይ፣
የት ጋር እንደሆነ ይታይ የእኛ ጥበብ መሰረቱ…፡፡
እናም እስቲ ታሪክ ይታይ፣ ይመርመር፣ ዘመናትን ያስረጁና የተሻገሩ ብራናዎቻችን ይውጡ፣የሺህ ዘመን የሃይማኖት፣ የጥበብ፣ የታሪክ፣ የሥልጣኔና የፍልስፍና ድርሳኖቻንን ይታዩይመርመሩ… በአክሱም ስልጣኔ፣ በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ትንግርት፣ በጎንደርበእነ ፋሲለደስ የስልጣኔ አየር ዝናዋ የናኘላት፣ እነዛ ፍቅርን በጥበብ አስውበው በቅኔያቸውናበማኅሌታቸው ሰማይ ሰማያትን ሰንጥቀው በመንፈሳቸው ጸባዖት የደረሱ፣ በፍቅር ጧፍ የነደዱበማሕሌታዩ ያሬድ መንፈስ የተነሱ እንደ ተዋናይ ያሉ የቅኔ የጥበብ ጉልላቶች እንደ አጥቢያኮከብ በደመቁባት ምድር ዛሬን ፍቅር የተራብን፣ ጥበብን የተራቆትን፣ ስለ ፍቅር የደከመንምንድነው ምክንያቱ የሚል ይመስለኛል ቴዲ…፡፡
ቴዲ በሙዚቃው ለታሪክ ያለውን ስሱነትና (sensitivity) እውቀትም (Indigenous Knowledge)አሳይቶናል፡፡ ተዋናይን ስንቶቻችን እናውቀዋለን ተብለን ብንጠየቅ የሚያስተዛዝበን ሳይሆንይቀራል፡፡ በተለይ ደግሞ ለዘመናችን ትውልድ ለአፉም ለልቡም ቅርቦቹ እነ አርሴናል፣ቼልሲ፣ ሜሲ፣ ሮናልዶ፣ እነ ፊፍቲ ሴንት እነ ቢዮንሴ፣ ወዘተ… የባሕር ማዶዎቹ ዝነኞች ናቸውእንጂ እነ ተዋናይን እነ ቅዱስ ያሬድን፣ እነ አጼ ፋሲልን ሊያስባቸው ወኔው ያለውአይመስልም፣ ኅሊናውንም ይደክመዋል እናስ እንዴት፣ ምን ሲደረግስ ሊያስባቸው ይችላል የኔትውልድ፡፡ በቅኔው የተራቀቀና በመንፈሳዊ እውቀቱ አንቱ ስለተባለው ስለ ተዋናይለመስማትም ሆነ ለማወቅ የታሪክ መዛግብትን ማገላበጥ ግድ ይላል፡፡ አሊያም ከቤተክርስቲያን ሊቃውንት አባቶች እግር ስር ቁጭ ማለት ያስፈልግ ይመስለኛል፡፡
ቴዲ በየትኛው መንገድ የሀገሩንና የቤተ ክርስቲያኑን የጥበብ እና የሥልጣኔ ከዋክብቶችንሊያውቅ እንደቻለ ባይነገረንም የትናንትናዎቹን የሀገራችንን ባለውለታዎችና የዘመንፈርጦች ማንነት ለማወቅ እና እንዲሁም ታሪኩን ለመመርመር ግን የተጋና የሰላ አእምሮእንደተቸረው/እንዳለው የግጥሞቹ መልእክቶች ይነግሩናል፡፡ እናም ከታሪካችንናከስልጣኔያችን መሰረት ከአክሱም ተነስቶ በጊዜና በታሪክ ሃዲድ ላይ አሳፍሮን በትላንትታሪካችን ውስጥ ራሳችንን እንድንመረምር፤ ራሳችንን እንድናይ ይወተውተናል፡፡ ለዚህደግሞ ምክንያቱ ይለናል ቴዲ ስለ ፍቅር ዜማው ውብ የግጥሞቹ ስንኞች፡-
. . .የኋለው ከሌለ የለም የፊቱ፣
ሳይራመድ በታሪክ ምንጣፍ፣
ሰው አይደርስም ከዛሬ ደጃፍ፡፡
በማለት ከታሪካችን ጋር እጅ ለእጅ በምናብ ሊያጨባብጠንና ሊያስተያየን ይፈልጋል፤ እናምያለ ትላንት ዛሬ የለም፣ ያለ ዛሬ ደግሞ ነገ አይታሰብም በሚል የመጣንበትና የተጓዝንበትንአኩሪና አሳፋሪ የታሪካችንን ምእራፍ ለማገላበጥ ለደከምን ለእራሱ እና ለእኛ ትልቅ ቁም ነገርያለው ምክር ያስተላልፋል፡፡ ይህ የከያኒው የግጥም ስንኝ የሮማውን ታላቅ የሕግ ሊቅ፣ፈላስፋና አስተማሪ የሆነውን የሲስሮን አባባል አስታወሰኝ፡- ‹‹ከመወለዳችን በፊት ያለውንታሪክ ካላወቅን ዕድሜ ልካችንን ሕጻን ሆነን እንቀራለን፡፡›› ታሪካችንን ለመመርመር እናከታሪካችን ለመማር የደከምን እኛ ዛሬም እንደ አዲስ ሰናፈርስ ስንጀምር ከመጀመር ሀ ሁሳንወጣ እንደ ህጻን ባለህበት እረገጥ የሆንበትና ታሪክን እንድንደግም የተፈረደብን ምስጢሩምን ይሆን በማለት ታሪክ ጠያቂ፣ የታሪክ ወዳጅ፣ ከታሪክ የምንማር እንድንሆን ያተጋናል፡፡
ከምንኮራበት ታሪካችንና ስልጣኔያችን ባልተናነሰ አንገት የሚያስደፋ ስማችንና ማንንታችንበዓለም ፊት በቀየረብን በበርካታ የራብ፣ የእርስ በርስ ጦርነትና መበላላት ታሪክ ዘመናትንውስጥ አልፈናል፡፡ እናም የመጣንበት መንገዱ ረጅም ዘመናቶቻችንም መከራ ሰቆቃና ዋይታ የነገሰባቸው ናቸው ሲል የትናንቱን ታሪክ ለመድገም የተፈረደብን ይመስል ታሪክ ደጋሚዎች እንድንሆን የሆንበትን እውነታ መመርመርና ማየት እንችል ዘንድ ትልቅ ጥያቄያጭርብናል፡፡ ዛሬም እግራችን መሄድ ተስኖት ቆመናል
የእርሱ ደጋፊዎች እንዳሉ ሁሉ የእርሱ ተቃዋሚዎች መኖራቸው ተፈጥሮአዊ ነው ነገር ግን በአሉባልታ የቴዲን ስራዎች ጥላሸት ለመቀባት የሚደረግ ትግል ወይ ቅናት ነው አልያም ለተቀማጭ ሰማይ ቅርቡ ነው እንደሚባለው ይሆናል፡፡
ለእምዬ ምንሊክ ያላቸው ጥላቻ ሰሞኑን ተቀስቅሶባቸው ያዙኝ ልቀቁኝ ሲሉ ከርመዋል አስገራሚው ነገር ምንሊክን ለመሳደብ ቴዲን ሰበብ ማድረጋቸው ነው ሌላው ደግሞ መረጃውን እኔ ለቅቄዋለው ብሎ ማንም ኃለፊነቱን እሰከዚች ሰዐት ድረስ ሳይወስድ እነርሱ ቴዲን እና ምንሊክን መዝለፍ የየእለት ተግባራቸው አድርገውታል፡፡
ምንሊክን ህዝቡ እምዬ ብሎታል ቴዲን ደግሞ የዘመናችን የሙዚቃው ንጉስ ብሎ ሰይሞታል
ደበበ ሰይፉ ጥሬ ጨው በሚለው ግጥሙ እንዲህ ነበር ለነፈዞች የገጠመው

ጥሬ ጨው – ደበበ ሰይፉ
————
መስለውኝ ነበረ ፣
የበቁ የነቁ
ያወቁ የረቀቁ
የሰው ፍጡሮች ፣
ለካ እነሱ ናቸው ፣
ጥሬ ጨው..ጥሬ ጨው
ጥሬ ጨዋዎች ፣
መፈጨት-መሰለቅ-መደለዝ-መወቀጥ-
መታሸት-መቀየጥ
ገና እሚቀራቸው ፣
“እኔ የለሁበትም !”
ዘወትር ቋንቋቸው ።

ለማንኛውም እኔም እንደ ደበበ ሰይፉ ሰሞንኛ የቴዲ ተቺዎችን ጥሬ ጨው ብዬ ሰይሜያቸዋለው፡

 

↧

የዝነኛው አርቲስት ቴዎድሮስ ምትኩ (ቴዲ) የቀብር ሥነ-ስርዓት የፊታችን ቅዳሜ በሜሪላንድ ይፈጸማል

$
0
0

teddy mitiku 2

(ዘ-ሐበሻ) ከቀናት በፊት ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ታዋቂው የሙዚቃ ሰው ቴዎድሮስ ምትኩ (ቴዲ) የቀብር ስነሥርዓት የፊታችን ቅዳሜ በሜሪላንድ እንደሚፈጸም ቤተስቦቹ ለዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ ገለጹ።

ኖቬምበር 11 ቀን 1955 ዓ.ም በአዲስ አበባ የተወለደው ይኸው ታዋቂ የሳክስፎን ሙዚቃ ባለሙያ ህይወቱ ያለፈችው ባለፈው  ቅዳሜ  ዲሴምበር 22 ቀን 2013 በዋሽንግተን ዲሲ መሆኑን ዘ-ሐበሻ ከቀናት በፊት መዘገቧ ይታወሳል።

በሕዝብ ዘንድ እንደተወደደ የኖረው ቴዲ የፊታችን ቅዳሜ  ጸሎተ ፍትሃቱ እና የቀብር ስነ ሥርዓቱ በሜሪላንድ ስለሚፈጸም አድናቂዎቹ በብዛት ወጥተው እንዲሸኙት ቤተሰቦቹ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

የጸሎትና ፍትሃቱ የሚደረገው ቅዳሜ ከጠዋቱ 9:30 በር ዕሰ አድባራት ደብረሰላም ቅድስት ማርያም ቤ/ክ ሲሆን አድራሻውም የሚከተለው ነው።
Re’ese Adbarat Debre Selam Kidest Mariam
The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church
1350 Buchanan St. NW, Washington, DC 20011

ከዚያም የቀብር ስነሥርዓቱ በThe Gate of Heaven Cemetery 13801 Georgia Ave. Silver Spring, MD 20906 ይፈጸማል።

ቴዲን ለመሸኘት የወጣው ፕሮግራም የሚከተለው ነው፦
teddy mitiku
Saturday, December 28, 2013
5:15 AM
Teddy Mitiku’s Hearse Arrives at Re’ese Adbarat Debre Selam Kidest Mariam The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. The church is located on 1350 Buchanan St. NW, Washington, DC 20011.
6:00 AM
The procession of Teddy Mitiku’s casket (carried by six Ethiopian Artists) and family into the church will take place from the entrance on Buchanan Street.
6:00 AM – 9:15 AM
Regular church service will be conducted
9:30 AM – 10:45 AM
Wake ceremony
10:45 AM – 11:15 AM
Memory sharing from family and friends in attendance.
11:15 AM – 11:45 AM
Various Ethiopian artists honor Teddy Mitiku
11:45 AM – 12:00 PM
Preparation to commence procession. Teddy Mitiku’s final resting place will be at The Gate of Heaven Cemetery at 13801 Georgia Ave. Silver Spring, MD 20906
12:05 PM
The Procession will start from the intersection of 16 Street and Buchanan Street, the Procession will turn right onto 16th St
The Procession enters next roundabout and take the 3rd exit onto 16th St/MD-390 N (Crossing into Maryland)
The Procession then turn right onto Georgia Ave and arrives its destination at the Gate of Heaven Cemetery on the right.
Attention: Maryland and the District of Columbia law require that all drivers who participate in a procession must turn both their headlight and hazard lights
1:30 P.M.
Once Teddy Mitiku’s casket arrives at the Gate of Heaven Cemetery, burial ceremony begins.
After we finally lay to rest Teddy Mituku, Funereal Reception takes place at The Blair Apartment -East (next to Giant) 1220 East-west Hwy, Room # 119 (Hospitality Suite), Silver Spring, MD 20910
Place of Mourning until Sunday, December 29, 2013:
The Blair Apartment (East)
1220 East-west Hwy,
Room #119 (hospitality suite)
Silver Spring, MD 20910

↧

አንድነትና የሚሊየንም ድምጽ ለነጻነት ንቅናቄ –አማኑኤል ዘሰላም

$
0
0

amanuelzeselam@gmail.com
ታህሳስ 15 ቀን 2006 ዓ.ም
 

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር፣ አቶ ይልቃል ጌትነት፣ በዉጭ አገር የሥራ ጉብኘት እያደረጉ እንደሆነ በስፋት እየተዘገበ ነዉ። ታዲያ «ስለ ሰማያዊ ብዙ እየሰማን፣ የአንድነት ፓርቲ ድምጽ ግን ምነዉ ጠፋ። የሚሊየነሞች ድምጽ ለነጻነትስ ወዴት ገባ ?» ብለን የምንጠይቅ ልንኖር እንደምንችል አስባለሁ። በዚህም ረገድ በአንድነት ፓርቲ ዙሪያ አንዳንድ ሃሳቦች ለአንባቢያን ለማካፈል እሞክራለሁ።

በቅድሚያ አንድ መረዳት ያለብን ነገር አለ። የአንድነት ፓርቲና እና ሰማያዊ ፓርቲ፣ ሁለቱም ተመሳሳይ የፖለቲካ ፕሮግራም ቢኖራቸውም ፣ ሁለቱም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለዉጥ ለማምጣት ቢታገሉም፣ የአሰራር ልዩነቶች አሏቸው። የአንድነት ፓርቲ፣ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ የትግሉ አካል እንደሆነ ቢያውቅም፣ መሰለፍ ብቻ በራሱ ምንም ሊያደርግ እንደማይችል ጠንቅቆ የተረዳ ደርጅት ነዉ። በዚህም ምክንያት ግብታዊ የሆኑ እንቅስቃሴዎችን ከማድረግ ብዙ ይቆጠባል። ሰልፎችም ሆነ ማናቸዉም አይነት ሰላማዊ እንቅስቅሴዎች ተጠንተዉ፣ በጥንቃቄና ዉጤት በሚያመጣ መልኩ መደረግ አለባቸው ብሎ ያማናል። ካለፈው የቅንጀት ስህተቶች ብዙ የተማረ ነው።

በመሆኑም ሰልፍ አልተደረገም ማለት እንቅስቃሴ የለም ማለት አይደለም። የአንድነት ፓርቲ በአሁኑ ወቅት እያደረጋቸው ያላቸዉን አራት በጣም አስፈላጊና መሰረታዊ ጉዳዮች እንዳካፍል ይፈቀድልኝ፡

1. አንድነት፣ ከሰኔ እስከ መስክረም የተደረገዉን የሚሊየኖችም ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴዎች፣ እንዲሁም የፓርቲዉ ጠቅላላ ስራዎች፣ ወደ ኋላ ተመልሶ ግምገማ እያደረገ ነዉ። «የቱ መስተካከል አለበት ? የቱ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ? ..»እየተባለ ፣ ጠቃሚ ትምህርቶችን ለማሰባሰብ እየተሞከረ ነዉ። ዝም ብሎ መሮጥ አይደለም። ቆም ብሎም ማሰብና እራስን መመርመር፣ ካለፉትን ተግባራት መማር ያስፈልጋል።

2. ፓርቲው በቅርቡ የአመራር አባላትን ይመርጣል። አብዛኞቹ አገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ ያሉ ድርጅቶች አንድ መሪ ነው ለዝንተ አለም የሚመራቸው። የአንድነት ፓርቲን መጀመሪያ ብርቱካን ሚደቅሳ፣ ከዚያም ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራዉ፣ ከዚያም ዶር ነጋሶ ጊዳዳ መርተዋል። አሁን ደግሞ ዶር ነጋሶን ለመተካት ሶስት እጩዎች የምረጡኝ ዘመቻ ላይ ናቸው። እነርሱም የፓርላማ አባል የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ ቀድሞ ፓርቲዉን ሲመሩ የነበሩትና በበርካታ አባላት እንደገና እንዲወዳደሩ ግፊት እንደተደረገባቸው የሚነገረዉ፣ አንጋፋው ኢንጂነር ግዛቸው እንዲሁም ኮንሴንሰን ቢልድ በማድረግና በአስተዋይነታቸው የሚታወቁት፣ በአሁኑ ወቅት ፓርቲዉን በፋይናንስ ሃላፊነት የሚመሩት፣ አቶ ተክሌ በቀለ ናቸው።ይህ በአንድነት ዉስጥ እየተደረገ ያለው ፉክክር ፣ በማንም የአገራችን ድርጅቶች ያልታየ ዴሞክራሲያዊ  ፉክክር ነዉ።

3. እርግጥ ነዉ ከአሁን ለአሁን ሕብረት ያስፈልጋል ተብሎ፣ ወደ ኋላ ከሚጎትትና ስራን ከማያሰራ ድርጅት ጋር ሕብረት አይፈጠርም። ሕብረት ሲፈጠር ለዉጤት መሆን አለበት። በዚህም ረገድ አንድነት ከዚህ በፊት አካል ከሆናቸው እንደነ መድረክ ካሉ ስብስቦች ጋር ያለዉን ግንኙነት እየፈተሸ ነዉ። በአንጻሩም ደግሞ ፓርቲውን ሆነ ትግሉ ወደፊት እንዲሄድ ሊረዱ የሚችሉ ፣ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ፣ የላይ ላይ ትብብር ሳይሆን የዉህደት እንቅስቃሴ እያደረገ ነዉ። ከዚህ በፊት እንደ ብርሃን ፓርቲ ያሉ ድርጅቶች ከአንድነት ጋር መዋሃዳቸው ይታወቃል። አሁን ደግሞ አንድነት ፓርቲ ከአንጋፋዉ መኢአድና በአሁኑ ወቅት አስደሳች እንቅስቅሴ በሜዳ ላይ አያደረገ ካለው ከአረና ጋር ለመዋሃድ ትልቅ ሥራ እየሰራ ነዉ።

4. ሰላማዊ ሰልፍ ሆነ ሌላም ሌላም እንቅስቅሴዎች እንዲሁ በግብታዊነት አይሰሩም። ጥናት፣ ጥንቃቄ፣ ዝግጅት ያስፈልጋል። የስሜት ትግል የትም አያደርሰም። ትግሉ የሰከነ፣ የበሰለና ዉጤት የሚያመጣ መሆን አለበት። የአንድነት ፓርቲ የሚሊየነም ድምጽ ለነጻነት በሚል ስም የጀመረው እንቅስቃሴ ክፍል ሁለት፣ ከአመራር አባላት ምርጫ በኋላ፣ ይታወጃል። ይህ እንቅስቃሴ አዲስ አበባ ዉስጥ ብቻ ያተኮረ ሳይሆን፣ በመላ አገሩቷ ያተኮረ፣ ትግሉን አንድ እርምጃ ወደፊት የሚወስድ እንቅስቃሴ ይሆናል። ለዚህም እንዲረዳ አባላት በሰላማዊ ትግል ዙሪያ የተለያዩ ስልጠናዎች እየወሰዱ ናቸው።

እንግዲህ አገር ዉስጥና ከአገር ውጭ ለምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እላለሁ። በአገራችን ሙስና የመስፋፋቱ፣ ዘረኝነት የመብዛቱ፣ የሕግ ስርዓት ያለመኖሩ፣ የኑሮ ዉድነቱ፣ የሰባአዊ መብት ረገጣዉ ፣ ኢትዮጵያ ለብዙሃኑ ሲኦል፣ ከገዢው ፓርቲ ጋር ግንኙነት ስላላቸው ብቻ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ሚሊየንር ለሆኑት ለጥቂቶች ገነት ለመሆኗ ምክንያቱ የፖለቲካዉ ችግር ነው። የፖለቲካ ችግርን ለማስተካከል ደግሞ የፖለቲክ ትግል ይጠይቃል። የአንድነት ፓርቲ ይህ ለሰላምና ለፍትህ የሚደረገዉን የፖለቲክ ትግል ለመምራት እየሰራ ነዉ።

የአንድነት ፓርቲ ከሁለት ወራት በፊት ባደረጋቸው አገረ ሰፊ፣ የሚሊየም ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴዎች፣ በአዲስ አበባ፣ በመቀሌ፣ በጎንደር፣ በባህር ዳር፣ በደሴ፣ በጂንካ፣ በአርባ ምንጭ፣ በወላይታ ሶዳ፣ በባሌ/ሮቢ ፣ በፍቼና በአዳማ ሰላማዊ ሰልፎች አድርጓል። በመቀሌ ሰልፉ ሊደረግ አንድ ቀን ሲቀረዉ የሕወሃት ባለስልጣናት «እንኳን አንድነት፣ ቅንጅትም መቀሌን አልደፈረም»በሚል የቅስቀሳ መኪናዎችን እና ማይክሮፎኖችን በማገታቸውና የአመራር አባላትን በማሰራቸው፣ ከአሥር አምስት ቀናት ቅስቀሳ በኋላ ሰልፉ ሊሰረዝ ችሏል። በባሌ/ሮቢ፣ ኦሕድዶች ሰልፉ ከመደረጉ አንድ ቀን በፊት፣ «ሰልፉን ካደረጋቸው ከፍተኛ ደም መፋሰስ ይሆናል» የሚል ዛቻ በመሰንዘራቸው ፣ ሕዝብን አደጋ ላይ ላለመጣል ሲባል፣ ሰልፉ ሳይደረግ ቀርቷል።

የአንድነት ፓርቲ በአዋሳ፣ በጋምቤላ፣ በወሊሶ፣ በድርደዋና በአሳሳም ሰልፎች ለማድረግ እቅድ ነበረዉ። ነገር ግን በገንዘብ ማነስ ምክንያት እነዚህ ከተሞች ሰልፍ ማድረግ እንዳልተቻለ ነው።

አሁንም ፓርቲዉ የተቻለዉን ለማድረግ የወሰነነ የቆረጠ ቢሆንም፣ ፓርቲዉ የሕዝብ ድጋፍ ከሌለዉ ሊያደርግ የሚችለው የተወሰነ ነዉ። በተለይም የገንዘብ አቅም ላይ ትልቅ ትኩረት መስጠት እፈልጋለሁ። እንዲሁ ለዉጥ ስለተመኘን ለዉጥ አይመጣም። አገር ቤት ያሉ ኢትዮጵያዉያን በጓዳና በሹክሹክታ ብሳታችንን መግለጽ ማቆም ይኖርብናል። ትግሉ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊን ተሳትፎ ይጠይቃል። ጠንካራ ፓርቲ ሲመጣ መቀላቀሉ ሳይሆን፣ አሁን ያሉትን፣  እንድ አንድነት ፓርቲ አይነቶችን ጠንካራ እንዲሆኑ ማድረጉ ይበጃል።

ዉጭ አገር ያለነው ፣ ምን እንኳን የመገደል፣ የመታሰር፣ የመዋከብ አደጋ ባያገኝንም፣ ቢያንስ ስራችን እና አፋችን መገናኘት ያለባቸው ይመስለኛል። «አገር ቤት ካሉት ድርጅቶች ለዉጥ ለምን አያመጡም» ብለን መናገርና መጠየቅ ሳይሆን፣ ለዉጥ እንዲያመጡ የነርሱ አካል ሆን ድጋፋችንን መስጠት ይጠበቅበናል። ሕዝቡ ካልተነሳና ካልተነቃነቀ በምን ሁኔታ ለዉጥ ሊመጣ አይችልም። ህዝቡ እንዲነሳ ሕዝቡ መሃከል ሆኖ ትልቅ ድርጅታዊ ሥራ መስራት ያሰልጋል። ይህን አይነት ድርጅታዊ ሥራ ለመስራት፣ ሕይወታቸው ለዚህ ሥራ አላልፈው ከሰጡ አገር ቤት ካሉ ጀግኖች ጎን መቆም ይኖርብናል።

እንግዲህ ለሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴ ክፍል ሁለት ከወዲሁ ሁላችንም እንዘጋጅ። ፓርቲዉን በገንዘባችን እንደግፍ። በገንዘብ ለመርዳትና ከሚሊዮኖች አንዱ ለመሆን የሚፈልጉ ከሆነ የሚከተለዉን ድህረ ገጽ ይጎብኙ !

http://www.andinet.org/

 

comment pic

 

 

↧
↧

ትንሽ ስለጃዋር መሀመድ _ ከዓለማየሁ መሀመድ

$
0
0

ሁለት ነገሮችን ላንሳ።

1.  የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል መሬት አንቀጥቅጥ ሆኖ ለሁለት ዓመት ገደማ ዘልቋል። በዚህ ትግል ውስጥ በሀገር ቤት ከስርዓቱ ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀው ደም ህይወታቸውን ገብረው ትግሉ በማይናወጥ ጽናት ላይ እንዲቆም ያደረጉት ብዙሃኑ ሙስሊሞች ዋጋቸው በክብር መዝገብ ላይ ምንጊዜም ወርቃማ በሆነ ቀለም ተመዝግቦ ይቀመጣል። ከእነሱ ባሻገር በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ትግሉ መሬት ይዞ  በሰከነ መልኩ እንዲጓዝ ያደረጉት አስተዋጽኦም የሚዘነጋ አይደለም። ጃዋር በዚህ ውስጥ ስሙ ሲጠቀስ ነበር። የሙስሊሞች ትግል ላይ ትንሽም ብትሆን አሻራው አርፎበታል። ያኔ ነው። በፊት። አሁንስ?

2.  የኦሮሞ ህዝብ ጭቆና ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ የተለየ ነው- አይደለም -የሚለው ክርክር ለጊዜው ይቆይና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ለ40 ዓመታት ሲያቀነቅነው የነበረውና ውጤት ሳይኖረው ዘመናት የቆየው ትግሉ አሁን ‘’የኦሮሞን ህዝብ ትግል በኢትዮጵያ ጥላ ስር’’ የሚለው ሀሳብ አሸንፎ ሲወጣ ጃዋር ብቅ አለ። መጀመሪያ ላይ በሳል በሆኑ፡ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ፡ የሰውን ልጅ በአንድ መነጽር የሚመለከቱ የሚመስሉ ሀሳቦች በጃዋር አፍ ውስጥ ይዋኙ ነበር። ይህም በተቀረው ኢትዮጵያውያን ዘንድም ጃዋር ምናልባት ያረጀውን የኦነግ ጠባብ ብሄርተኝነት ከመቃብር አስቀመጦ የኦሮሞን ህዝብ ከዕውነተኛ ድል የሚያቀርብ አዲስ መንገድ ይጀምራል የሚል ብጣቂ ተስፋ ውስጣቸው የነበሩ ጥቂቶች አልነበሩም። ከመነሻውም የተጠራጠሩት፡ የተደበቀው ማንነቱ አንድ ቀን ይወጣል ብለው በጥርጣሬ ሲመለከተቱት የነበሩት ቁጥራቸው የትየለሌ ነበር። ሆኖም እኔም ሆንክ ጥቂቶች ጃዋርን እንደ አብሪ ኮከብ መመልከታችን አልቀረም። አሁንስ?

ጃዋር አሁን አይሰማም። መስማት የሚፈልገው የፈለገውን ብቻ ነው። በየአዳራሹ የሚሰማው ጭብጨባ ሰርቆታል። ቀልቡ አሁን ከሚኒሶታ እስከ ለንደን በተዘረጋው የ’ኦሮሞ ፈርስት’ ቅልጥ ያለ የወቅቱ ነጠላ ዜማ ላይ ሆኑዋል።

1. የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል በእፎይታ ጊዜ ላይ ቢሆንም የጃዋር ‘ኦሮሞ ፈርስት’ በይፋ ከታወጀችና ‘ሜንጫ’ዋ በሚኒሶታ መድረክ ከተስተጋባች በኋላ የሙስሊሞች ትግል ላይ መጠነኛ ተጽእኖ መፈጠሩ አልቀረም። የሙስሊሙን ትግል የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል አድርገው የተሰለፉ ወገኖች በጥቂቱ ማፈግፈጋቸው በመጠኑ ይታያል። ሜንጫ የሚለውን ቃል ጃዋር ሚኒሶታ ላይ ካፈነዳት ወዲህ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ እንኳን ውዥንብር ተፈጥሯል። እናም የሟችዋ ሚካያ በሃይሉ ዜማን ልዋሰው- “ሸማመተው”::  ህወሀት ሸመተ:: ትግሉ እንዲደበዝዝ ቀን ከሌት ይመኝ የነበረው ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ- ሸማመተው!!

2.  ከምንጊዜውም በላይ የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነቱን ለማሳየት፡ በጋራ ወደ ምር ነጻነት ለመምጣት እጅ ለእጅ እየተያያዘ ያለበት ወቅት ላይ እነጃዋር የኦሮሞ ብሄርተኝነትን ወደ ጠባቡ ጽንፍ ወስደውት ዘራፍ ማለት መጀመራቸው በተወሰነ ደረጃ ለህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ከሰማይ የወረደ አዱኛ ሆነለት:: አሁንም ሚካያ ትላለች -“ሸማመተው” – ህወሀት ሸመተ::

እነ ጃዋር እየተናገሩ ነው:: ‘ኦሮሞ  ፈርስት’-‘ ማይ ካንትሪ ኢዝ ኦሮሚያ’ ::  የህወሀት የፌስቡክና ትዊተር ሰራዊቶች ስማቸውን በኦሮምኛ ለማድረግ ከብርሃን ነበር የፈጠኑት:: እናም ‘ኦሮሞ  ፈርስት’  መፈክራቸው ሆኖ አጼ ሚኒሊክ ላይ እርግማናቸውን ውእግዝ ከማርዮሱን እያዘነቡት ነው።

ጭብጨባው ቀልጧል። ነጠላ ዜማው ሰማይ ምድሩን አድምቆታል፡፡ እነጃዋር በህወሀት ነጠላ ዜማ ዳንሱን እያቀለጡት ነው። የሚሰማ ጆሮ የላቸውም። ልባቸው ሸፍቷል። አውቀው ይሁን ሳያውቁት ከህወሀት መንደር ዘልቀው የልፊያ ፖለቲካውን ተያይዘውታል። ጭብጨባ ክፉ ነው። ላላወቀበት ስካር ነው።

ሰሞኑን ከጨፌ ኦሮሚያ አንድ መረጃ ደርሶኛል። ሳይላመጥ አይቀርብም በሚል ለጊዜው ይዤዋለሁ። እነጃዋርን የተመለከተ ነው። ምናልባት መረጃውን በማስረጃ ማስደገፍ ከቻልኩኝ በድብቅ የተፈጸመውን የእነጃዋርንና ህወሀትን ጋብቻ ይፋ አደርጋለሁ።

እስከዚያው ጩኧቱን እየሰማን እንቆይ። መልካም ጋብቻ የምንልበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።

comment pic

↧

ሰላማዊ ትግል እና ባህሪያቱ: ስልጠና ክፍል አምስት፥ ከ1924 – 2002 በኢትዮጵያ የተደረጉ ምርጫዎች ግምገማ –በግርማ ሞገስ

$
0
0

በግርማ ሞገስ
ቅዳሜ ታህሳስ 12 ቀን 2006 ዓ.ም.

Girma Moges

ግርማ ሞገስ

የስልጠና ክፍል አምስት ግብ በዐፄ ኃይለስላሴ ዘመነ መንግስት (1924-1967)፣ በደርግ ዘመነ መንግስት (ከ1967 – 1983)፣  (3ኛ) በህውሃት/ኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (1983 – 2002) የተደረጉትን ምርጫዎች በአጭር በአጭሩ መጎብኘት እና  መገምገም ነው። ምርጫ 97 ግን በርከት ያሉ ትምህርቶች በመለገሱ ሰፋ አድርገን እንጎበኘዋለን።
ምስጋና፥ ይኽን ግምገማ ሳዘጋጅ ከሌሎች መረጃ ምንጮች በተጨማሪ “ግንቦት 7” በሚል ርዕስ ክፍሉ ታደሰ ስለ ምርጫ 97  ዝግጅት፣ ሂደት እና አፈጻጸም የጻፈውን መጽሐፍ አና “ነፃነት እና ዳኝነት” በሚል ርዕስ ስየ አብርሃ ከጻፈው መጽሐፍ ውስጥ  ስለምርጫ 97 አንስቶ ምክሮች የሚለግስበትን ጠቃሚ ምዕራፍ ተጠቅሜያለሁ። እንዲሁም የታሪክ ባለሙያዎቹን የባህሩ  ዘውዴን እና የተክለ ፃድቅ መኩሪያን መጽሐፍቶች ተጠቅሜያለሁ። ለሁሉም ምስጋናዬ ገደብ የለውም።   – ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ–

↧

የሳዑዲ ጉዳይ፡ “31.700 በላይ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች ከአሰሪዎቻቸው ጠፍተዋል! “

$
0
0

ነብዩ ሲራክ ከሳዑዲ አረቢያ

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)

የማለዳ ወግ … የተረሱት ኢትዮጵያውያን የኮንትራት ሰራተኞች በጭንቁ ቀን! 

“31.700 በላይ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች ከአሰሪዎቻቸው ጠፍተዋል! ”
እለተ ሃሙስ ታህሳስ 17 2006 የወጣው አረብ ኒውስ ” Over 31,000 Ethiopian maids ran away “ሳለፍናቸው አመታት ወደ ሳውዲ መጠው ከነበሩት ኢትዮጵያን መካከል ከ 31 ሽህ በላይ የቤት ሰራተኞች ከአሰሪዎቻቸው ጠፉ !” የሚለውን ዜና የሳውዲ መንግስት ስታስቲክ መረጃ ጠቅሶ አስነበበን ። አረብ ኒውስ ያስተላለፈውን መረጃ ካነብኩ ትዝ ያለኝ በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች እንደ ጨው የተበተኑት በኮንትራት ስራ የመጡ የተረሱት በኮንትራት ሰራተኝነት ከቤተሰብ ጀምሮ በደላላ ፣ በመንግስት ሃላፊዎች ብልሹ አሰራር እዚህ በሰው ሃገር ለከፋ አደጋ የተዳረጉት የኮንትራት ሰራተኞ እህቶች ጉዳይ ነው ። አዎ የእኒህ እህቶች መዳረሻ ባለመታወቁ አበሳቸው ዘልቆ ቢያሳስበኝ የማለዳ ወጌ ቅኝት ለማድረግና የማውቀውን መረጃ ለማስጨበጥ ብዕሬን ለማንሳት ተገደድኩ …

“ከጨለማው ህዳር” እስከ ታህሳስ አጋማሽ …

በህዳር መባቻ ግፍ ተጭኖናል የዘንድሮን ህዳር ጨለማ ማለታችን ቢያንስ እንጅ አይበዛበትም። በጨላማው ህዳር ድህነትና የኑሮ ውድነት በለምለም ሃገራችን ተደላድለን እንዳንቀመጥ ያደረገን ስደት ዛሬ የከፋ ሆኗል። እንዲከፋ ምክንያቶቹ ብዙ ቢሆንም በአቋራጭ ኑሯቸውን ለመቀየር የቋመጡት ህገ ወጥ አንዱ መሆኑና ይህም የጥቂቶች ባላስፈላጊ ስራ መሰማራት ስማችን አክፍቶት ለሃጣን የመጣው ለጻድቃን እንዲሉ በላባቸው ለሚያድሩት መፈናቀል ምክንያት መሆኑን ሳልጠቅሰው ማለፍ አልወድም ። እናም ዛሬ የመቶ ሽወች ኑሮ ተናግቷል! በጨለማው ህዳር!

በጨለማው ህዳር በዋና ከተማዋ በሪያድ የመንፉሃን ግርግር ተከተለ። የታየው ሁከት የብዙዎቻችን ትኩረት ሳበው! ትኩረቱ ያተኮረውህጋዊ ሰነድ የሌላቸው በተለይም የመንን ድንበር ተሻግረው ፡ ሃጅና ኦምራን ታከው የመጡት ዜጎች ጉዳይ ሆነ ! በግርግሩ የታየውን ጭካኔ በመፍራት የመንፉሃ ነዋሪ ያገሬ ሰው ጎጆውን እያፈራረሰ ሃገሩን ጥሎ ወጣ … ተሸኘ ! የሳውዲ መንግስትን ጨምሮ የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ባልጠበቁት ሁኔታ እዚህ ባደረሰን ሁለት ወር በተጣጋው ጊዜ ወደ 160 ሽህ የሚገመት ወገን ወደ ሃገሩ መግባት ከአስገራሚም አስገራሚ ነው ተባለ ። ከሪያድና ከምዕራቡ የሳውዲ ክፍል አንዳንድ ከተሞች የወጣውን ነዋሪ ብዛት የተመለከተ ባይተዋር ቁጥሩን በአግርሞት ቢመለከተው አያስገርምም ። እኛ በሳውዲ ውስጥ የባጀን የከረምን ግን “ጅዳ መች ተነካና ትገረማላችሁ ፣ ጀዛን ፣ አብሃ ፣ ከሚስ ምሸት ፣ ጣይፍና እና በሌላ ሌላው የከተመው ኢትዮጵያዊ መች ተነካና ትገረማላችሁ ? ” ማለት ያዝን … በቀቢጸ ተስፋ ወደ ሃገር መግባቱን አሻፈረኝ ያለው አድፋጩን ሰነድ የሌለውን የተጨነቀ ወገን ” ከሳውዲ ውጡ ” ከሚለው ጋር ሌላ ተደጋግሞ የተነገረ ግን ስላልተቀበልነው ልብ ያላልነውን መረጃ ቆንስልና ኢንባሲዎች ይዘውት ብቅ አሉ ። በቀጣዩ መጠነ ሰፊ የማጣራት ዘመቻም ከአሰሪው (ከከፊሉ) ጋር የማይሰራ እንደ ህጋዊ ስለማይቆጠር የሳውዲ መንግስት በፈቃደኝነት እጃቸሁን ሰጥታችሁ ወደ ሃገር ግቡ ሲል ደጋግሞ አስታወቀ ። ወደ ሃገር መስደድ እንደተጠናቀቀ አንወጣም ባሉት ላይ ፍተሻ በማድረግ በእስራትና በገንዘብ እንደሚቀጣ ኢንባሲና ቆንስል መስሪያ ቤቶች ሲያስታውቁ ወሽመጡ ያልተቆረጠ አለ ለማለት እቸገራለሁ ። እንዲህ እያልን የቆጥ የባጡን እያነሳን እየጣልን “ወደ ሃገሩ መግባት ሲገባው ሳይገባ የቀረው ቁጥር 80 ሽህ ፣100 ሽህ ፣150 ሽህ ይደርሳል !” ያለን ስነዘባራ መንፉሃ ዳግም በፍተሻ ትናጥ ያዘች! ረቡዕ ታህሳስ 16 2006 …

ለአንድ ማለዳ ወግ ቅኝቴ ይሆን ዘንድ ነፍሴ ፈቅዳለችና እናወጋዋለን!

ከጅዳ የሽሜሲ ጊዜያዊ ማቆያ የሚደርሰኝ ሮሮ !

“የሳውዲ መንግስት ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው ሳውዲን ለቀው አንዲዎጡ ያስተላለፈውን እና የኢትዮጵያ ኢንባሲና ቆንስለወ መስሪያ ቤቶች ዜጎች ሀጉን አክብረው ወደ ሃገራቸው እንዲወጡ
ያስተላለፉትን ተደጋጋሚ ማሳሰቢያዎች በመረዳት ወደ ሃገር ለመግባት ወደ ሽሜሲ መጠለያ በመሄድ እጃችን የሰጠን ዜጎች እየተንገላታን ነው! ” በማለት ሮሮና ቅሬታቸውን ያቀረቡ ወገኖች መጠለያ እንደገቡ በኢትዮጵያ መንግስት የመጓጓዣ ሰነድ የተሰጣቸው ቢሆንም የሳውዲ ፖስፖር ሃላፊዎች የቀረበላቸውን ሰነድ በማጣራት የመውጫ ሰነድ ለመስጠት አንግልት አያደረሱባቸው መሆኑን ገልጸውልኛል። ጉዳያቸውን ለማስፈጸም በአውቶቡስ ላይ እና በመጠለያው ግቢ ውስጥ ተበትነው በመጠባበቅ ላይ እንደሆኑ የገለጹልኝ እኒህ ወገኖች የአቅመ ደላማ ሴቶችና ህጻናትን እንግልት ከግምት ውስጥ በማስገባት የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ከሚመለከታቸው የሳውዲ መንግስት ሃላፊዎች ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን ትብብር ያደርጉላቸው ዘንድ ጠይቀዋል።

እኒሁ ሮሯችን ለሚመለከታቸው እንዳሰማ የተማጸኑኝ ወገኖች ወደ ጅዳ ቆንሰል ሃላፊዎች ስልክ ደውለው ስልክ ስለማያነሱ ወደ እኔ መደወላቸውን የገለጹልኝ ሲሆን ወደ ሃገር ግቡ ተብለን ወደ ሃገር እንግባ ባልን እንግልት ሊደርስብን አይገባም ሲሉ ” አሁን በደል እያደረሰብን ያለው ሳውዲ ኢሚግሬሽን መፍትሄ እንዲሰጠን ዲፕሎማቶች የተቻላቸውን ያድርጉልን! ” ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ። በሌላ በኩል ወደ መጠለያው ገብተው አስፈላጊውን ሰነድ ያሟሉ አንዳንድ ነዋሪዎች መካከል ሻንጣችን ጠፋብን የሚሉና ከአንድ ሻንጣ በላይ እንዳይዙ የተከለከሉ ነዋሪዎችም ተመሳሳይ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

ጉዳዪን ለማሳወቅና ዝርዝር ማብራሪያ ለማግኘት ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊ ወደ አቶ ዘነበ ከበደ እና ወደ ምክትላቸው አቶ ሸሪፍ ስልክ በመደወል ያደረግኩት ሙከራ ዛሬም አልተሳካም!

ሰላም ለሁላችሁ ይሁን!

ነቢዩ ሲራክ

↧

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ምእመናን “የሕዝብ ድምጽ ይከበር”ሲሉ መግለጫ አወጡ

$
0
0

የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ በገለልተኝነት እንዲቆይ በሕዝብ ድምጽ ብልጫ መወሰኑ ይታወሳል። ሆኖም ግን ይህን ውሳኔ የቤ/ክርስቲያኑ ካህናት ለመቀልበስ ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸውን በመግለጽ ለሰላም እና ለአንድነት የቆሙት ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ምእመናን የሚከተለውን መግለጫ አውጥተው በትነዋል።

12/26/2013

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ፤አሜን!

ለሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ምዕመናን

የሕዝብ ድምጽ ይከበር!!! የምንኖርበትን አገር ሕግና ሥርዓትም እናክብር!!!

deb

ባለፈው ዲሴምበር 15/2013 ዓ.ም የቤተክርስቲያናችን ጠቅላላ የአባላት ጉባኤ የደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የአስተዳደር ገለልተኝነት አስመልክቶ ባለበት እንዲቀጥል በከፍተኛ የአብላጫ ድምጽ መወሰኑ ይታወቃል። ይህም ታሪካዊና አርአያ የሆነ፤ ዲሞክራሲያዊ አሰራር የሰፈነበት ስብሰባ ይበል የሚያሰኝ ነው።

የሕዝብ ውሳኔም ከማንምና ከሁሉም በላይ ስለሆነ ማክበርና ማስከበር ደግሞ የሁላችንም ኃላፊነት ነው። ይሁን እንጂ አንዳንድ የአስተዳደር ቦርድ አባላት ድርሻና ኃላፊነታቸውን በቅጡ ያልተረዱ ካሕናት ይህንን የሕዝብ ውሳኔ በተዛባ መልክ በመተርጎም የተላለፈውን ውሳኔና ወደፊት ቢደረጉ ይጠቅማሉ ተብለው በሀሳብ ደረጃ የቀረቡትን በመደባለቅ ሰላምና አንድነትን ለማወክ የሚደረገው አካሔድ እጀግ አሳዝኖናል አስቆጥቶናል።

በተለይም የቤተክርስቲያኑ ተቀዳሚ ካህን/ መንፈሳዊ አባት ከኃላፊነታቸው ውጪ የጠቅላላው ስብሰባ ውጤትን ካሕናቱ ባቀረብነው ሃሳብ መሰርት ነው የተወሰነው በማለት ሕዝቡ ከወሰነው ውሳኔ በተዛባ መልኩ መናገራቸው የሕዝብን ድምጽ እንደመናቅ ሆኖ አግኝተነዋል። ሕዝቡ በምን ላይ ድምጹን እንደሰጠ ጠንቅቆ ያውቀዋል። የስብሰባውንም ውጤት ለሕዝብ የመግለጽ ሥልጣንና መብት ያለው የቦርዱ ሊቀመንበር ብቻ ናቸው።

በቤተክርስቲያናችን የመተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 6 ክፍል 3 ፊደል ’ሀ’ ተ.ቁ. 6 ላይ የቤተክርስቲያኑ ይፋዊ/ኦፊሴሊያዊ/ ቃል አቀባይ የቦርዱ ሊቀመንበር መሆኑን በግልጽ ይደነግጋል። በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 7 በፊደል ‘ሠ’ ላይም የቤተክርስቲያኑ ተቀዳሚ ካህን እንደማንኛውም የባላአደራዎች ቦርድ አባልነታቸው ለቤተክርስቲያኑ መተዳደሪያ ደንብ ድንጋጌዎች ሁሉ ተገዢ ናቸው ይላል። ስለዚህ ይህ አካሔድ በአስቸኳይ ሊታረም ይገባዋል እንላለን።

ከዚህም በተጨማሪም በሥርዓተ ቅዳሴ ም.2 ቁ 43 ላይ ማንም ቅዳሴውን ማወክ እንደማይገባው እንዲህ በማለት ይገልጻል። ‘ ክቡር ሚስጢርን ለመቀበል የተሰበሰቡ ምእመናን ሁሉ የእግዚአብሔርን ነገር ለመስማት ከቤተክርስቲያን ውስጥ በጸጥታ ይቁሙ። የሚናገርም የሚስቅም አይኑር፤ቤተክርስቲያን የነገር ቦታ አይደልችምና የጸሎት ቦታ ናት እንጂ። ’ ይህንን የሚያውቁ ካህናት ግን የቤተክርስቲያናችንን ሰላምና አንድነት ለማናጋት የሕዝቡን ውሳኔ ላለመቀበል ከሚያንገራግሩ ሰዎች ጋር ወንጌል እየተሰበክ በመቅደስ ውስጥና ከመቅደስም በመውጣት ስብሰባ በማድረግ ቆመንለታል የሚሉትን ሥረዓተ ቅዳሴ ራሳቸው ሲጥሱት ተስተውለዋል። ይህም ድርጊት ፈጽሞ መደገም የማይገባው ነው በማለት እንመክራለን።

የምንኖርበትን አገር ሕግና ሥርዓት ተከትሎ በሰላም እያመለከ ያለን ግለሰብም ሆነ ስብስብ በማንኛውም መንገድ መረበሽና ሰላምን ማደፍረስ፣ ረብሻን ማነሳሳትና ከሥረዓት የወጣ ድምጽ ማሰማትም ሆነ ተቃውሞ ማድረግ በአሜሪካ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ 9/42 መሰረት የሚያሰቀጣ ነው።

ምንም እንኳን ክርስትና ወንድምን/እህትን በአለማዊ ፍርድ ቤት ከሶ ማስቀጣትን ባይደግፍም ለቤተክርስቲያናችን ሰላምና ሥርዓት መከበር ስንል ከሥርዓት በመውጣት ሰላማችንን ለማደፍረስ

የሚሞክሩትን ሁሉ ለሕግ አካላት የምንከስ መሆኑን አበክረን እናስገነዝባለን። ሕግን አለማወቅ ከቅጣት አያድንም እና!

በሕዝብ በተላለፈው ውሳኔም ሆነ በቤተክርስቲያኑ አስተዳደር አቋም ላይ ቅሬታ አለኝ የሚል ሁሉ ይግባኙን አግባብንት ላለው አካል በሕጋዊ መንገድና ሥርዓትን በተከተለ መልኩ ብቻ ማቅረብ ይኖርበታል። ካሕናቱም ቢሆኑ በዚህ አገር የቤተክርስቲያናት ማቋቋሚያ ሕግጋት የሚመሩና የሚተዳደሩ እንጂ አሜሪካን አገር ላይ በሥራ ሊውል በማይችል የኢትዮጵያ የቤተክርስቲያን ማስተዳደሪያ ደንብ መሰረት የሚተዳደሩ እንዳልሆኑ ሊያውቁ ይገባል።

ስለሆነም የክርስትና ሕይወታቸው ብቻ ሳይሆን ሥጋዊ ሪከርዳቸውና ሕይወታቸውም ቢሆን ችግር እንዳይገጥመው ሊያስቡበት ይገባል እንላልን። ሕግን ባለማወቅ ወይንም ባለመረዳት በሌሎች አካባቢዎች ሁከት በመፍጠር በቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰው ሥርዓት አልበኝነት በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይ ፈጽሞ እንዲከሰት አንፈቅድም።

ለሰላምና ለአንድነት የቆሙ ምእመናን

↧
↧

እኛና እነሱ/ ዝቅ እንበል/ በጌዲዮን ከኖርዎይ

$
0
0

እኛና እነሱ/ ዝቅ እንበል/

ጌዲዮን ከኖርዎይ

Norway

በአለም ላይ ካሉ ሃገሮች ውስጥ ስልጣን የሌለበት ሃገር ቢኖር ወይም ባለስልጣኑ ህዝብ የሆነበት ሃገር ቢኖር ሳላጋንን ኖርዎይ የምትባለው ሃገር ናት ማለት እችላለሁ፥፥ በግልፅ ህዝቡ የሚፈልገውን፥ ያስተዳድረኝ እገዛለታለሁ ብሎ አምኖ ድምፁን የሚሰጥለት መሪ፥፥ መሪውም ከልቡ እራሱን ዝቅ አርጎ ለሃገሩ፥ ለወገኑ የሚሰራበት ሃገር፥፣ ህገመንግስቱ ወይም በኖርዌጅያኑ አጠራር /GrunnLov/ ለሁሉም እኩል የሚሰራና ተፈፃሚ የሚሆን፥፥

በቃ ዋናው ነገር ህገመንግስቱን አትንካ ነው፥፥
አስታውሳለሁ በአንድ ወቅት የአለም መንግስታት ተባብረው ቢንላዲንን ለመደብደብ ብለው አፍጋኒስታንን በሚደበድቡበት ወቅት የኖርዎይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተለያየ የስራ ጉዳይ በሚል በብዛት ወደ አፍጋኒስታን ይመላለሱ ነበርና እዛም ሲመላለሱ በአፍጋኒስታኖቹ ባህል ስጦታ የተለመሰ ነገር በመሆኑ ለካ አቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርዬ አንድ ምንጣፍ በስጦታ አጊንተው ሲመለሱ ስጦታው ወደድ ያለ ሆኖ እያለ ለኖርዌጂያን ግብር ስብሳቢ ቢሮ ወይንም /tax Administration/ ማስመዝገብ ሲገባቸው ዘንግተውት በኖርዎይ ትልቅ መነጋገሪያ ርእስ ሆኖ ሚዲያዎች ቁም ስቅላቸውን ሲያበሉአቸው ነበር፥ እንዲሁም ባንድ ወቅት የትራንስፖርት ሚኒስትርዋ በአንድ ወቅት አነስተኛ መርከብ ለመመረቅ ተጋብዘው በሄዱበት ወቅት ከአንድ ባለሃብት የእጅ ሰንሰለት የወርቅ በስጦታ አጊንተው እሳቸውም ዋጋው ውድ መሆኑን በለመረዳት ይመስላል ሳያስመዘግቡ በመቅረታቸው ሚዲያዎች ነገሩን ይደርሱበትና ካራገቡት በኋላ ታክስ አስቆርጠውባቸዋል ሚኒስቴርዋም ስጦታውን በመቀበላቸው እንደተፀፀቱ ለህዝባቸው ተናግረዋል፥፥
አሁን ግን ይህችን አጭር ፅሁፍ ለመፃፍ ያነሳሳኝ ከዚሁ ከኖርዎይ ሳልወጣ በዚህ በፈረንጆች ገና ዋዜማ በኖርዎይ ውስጥ ተሆነውን በሃገራችን ህልም ሳይሆን ቅዠት ወደሆነብኝ ነገር ልውሰዳችሁ፥፥
ከሶስት ወር በፊት በሴፕቴምበር 2013 በኖርዎይ በተደረገው የጠቅላይ ሚኒስቴር ምርጫ ተሸንፈው ስለጣናቸውን ያስረከቡት በኖርዎይ ምናልባትም ቁጥር አንድ ተወዳጅ ናቸው የሚባልላቸው የንስ ስቶልተንበርግ እንደውም ለምርጫው ጊዜ ታክሲ ሾፌር ሆነው ቅስቀሳ ሲያረጉ በነበረበት ጊዜ በኢሳት፥ በቢቢሲ የተዘገበላቸውhttp://ethsat.com/video/esat-kignet-taxi-shofieru-prime-minister/ የነበሩት ጠቅላይ ሚኒስቴር ለአሁኑ ገና በአል ዋዜማ ስራ ከለቀቁ በኋላ የመጀመርያ ስራቸው ያረጉት የገና ዛፍ መሸጥ ነበር፥፥
ዜናውን ሳየው ብዙም አልደነገጥኩም፥ ግን ቅናት አደረብኝ እንደውም ተስፋ ነው የቆረጥኩት፥፥
ሰውዬው እንዳልኩት በአንድ ወቅት በተለይ ኢኮኖሚ ክራይስስ ተብሎ አውሮፓውያኑ እየተጨናነቁ በነበረበት ወቅት ሃገራቸውን በብቃት ችግሩ ባጠገቧም ሳይደርስ ስላሳለፉት የሃገሪቷ ቁጥር አንድ ተወዳጅ ሰው ከንጉሱም በላይ ተብሎ ሚዲያ ላይ ወቶ እንደነበር አስታውሳለሁ፥ ሃብታም ናቸው፥ እውቀት አላቸው በነገራችን ላይ አባታቸውም የኖርዎይ ጠቅላይሚኒስቴር ሆነው አገልግለዋል፥፥ ብቻ ለማጠቃለል ያህል ሰዎቹ ከራሳቸው በላይ የሚያስቀድሙት ብዙ ነገር ዓላቸው፥ ህዝባቸው፥ ሃገራቸው፥ አላማቸው፥ ግባቸው፥ ሌላም ሌላም
እንግዲህ እስካሁን ስለ እነሱ ነው ያወራሁት ግን እኛስ?

እኛ ማን ነን?
ለምንድነው የምንታገለው?
ለማን ነው የምንታገለው?
ምንድነው አላማችንና ግባችን?
ወደኛ ሲመጣ ይህ ጥያቄ ለሁላችን በግለሰብ ደረጃ መልስ ሊያገኝ የሚገባው ጥያቄ ይመስለኛል፥፥
ዝቅ እንበል!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!

↧

የዘፋኞቻችን ሞራልና ስብእና

$
0
0

ከጥበቡ ተቀኘ

የሃገራችንን የሙዚቃ ስራ ድሮ በሽክላ ኋላ ላይ በካሴት አሁን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በሲዲ ታትሞ ገበያ ላይ ሲቀርብ እንገዛና ከማዳመጥና ከማጣጣም አልፈን እንደ ቅርስ በየቤታችን የምንወዳቸውን ዘፋኞች ስራ እናስቀምጥ ነበር:: ከዚሁ ጉዳይ ጋር ተያይዞ የለመድናቸው የሙዚቃ ቤት ስሞችም ነበሩን ታንጎ ፣ አምባሰል ፣ ሶልኩኩ ፣ ኤሌክትራ ፣ ዜድ… አድራሻችን ከመርካቶ ዝቅ ብሎ፣  ከአውቶቡስ ተራ አጠገብ ፣ አንዋር መስጊድ ፊት ለፊት… ግጥም ይልማ ገብረአብ ፣ ዜማ አበበ መለሰ ፣ ከመድረክ የቀረጸው ከድር ጭቅሳ… የሚሉ ጽሁፎች በየካሴትና ሲዲው ላይ ይታይ እንደነበር ካስታወስኩኝ በኋላ ወደ ዛሬ ዋናው ጉዳዬ እገባለሁ::

radar_teddy_afro_back_smiling

ኣሁን በተለይ ያለፉትን ሶስትና አራት አመታት ትላልቅ የማስታወቅያ ባነሮች ላይ የዘፋኙ ፎቶ አጠገብ በጣም በትልቁ ሜታ ቢራ፣  ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ፣  በደሌ ቢራ፣  ባቲ ቢራ፣ ሐረር ቢራ… የሚል ማስታወቅያ ማየት የተለመደ ነገር ሆኗል::በጣም የሚገርመው ደግሞ ዘፈኖቹን ልንሰማ ሲዲውን ስንገዛው ከሲዲው ጀርባ ይሄንኑ የቢራ ማስታወቅያ ቤታችን ይዘነው እንመጣለን:: እኔ ይሄንን ካየሁ በኋላ ለልጆቼማ ኑ በቢራ ተደሰቱ የሚል ማስታወቅያ ያለበት ሲዲ ይዤ ላለመግባት ወስኜ መግዛቱንም ትቼዋለሁ:: ሙዚቃው በሙዚቃ ቤት ብቻ ሳይሆን በቢራ ፋብሪካዎች ስፖንሰርነት እየወጣ እንደሆነም በሰፊው ማየት ይቻላል:: ለመሆኑ ሙዚቃው ካለ ቢራ ማስታወቅያ መሰራት አይችልም? ዘፋኞቹስ ለልጆች እና ለሚያድጉ ወጣት ጎረምሶች የወደፊት እጣ እንዳይናጋ ወይ እንዳይበላሽ በመቆርቆር ይሄ የሚያስነውር አካሄድ አይሆነንም ፣ አይበጀንም አይሉም እንዴ? ነፍሱን ይማርና ተፈራ ካሳ ለህዝብ ትምህርቱን በዘፈን እንዲ ነግሮን አልፏል:
ShewandagnHailuAddisAlbum
በመጠጥ ደስታ ይገኛል ብላችሁ

መጠን አትለፉ ትቃጠላላችሁ

ለነገሩ ቴዲ አፍሮ ወዶ ከፈረመና ከሰራ በኋላ እኔ አልፈልግም ፣ ይሄንን ጉዳይ እቃወማለሁ ፣ እንደውም እከሳለሁ ብሎ ቡራ ከረዩ አብዝቶ እንደነበር ይታወቃል ግን የፈጠረው ምንም ነገር እንደሌለ መገንዘብ ችያለሁ:: ይልቁንስ አሁን ከቅርብ ቀን በፊት ልጆች የኔን ፎቶ ከቢራ ጋር እንዲያዩት አልፈልግም ፣ ለወጣቶች ጥሩ አርአያ መሆን እፈልጋለሁ ሲል የነበረው እራሱ ቴዲ ለቢራ ፋብሪካ ፈረመ የሚል ዜና አንብቤ ወይ ስብ እና እያልኩ ነበር:: ዘሪቱ ከበደ በዚህ ከቢራ ፋብሪካ ስፖንሰርነት ጋር በተያያዘ ጉዳይ በጣም ጠንካራና የምትመሰገን ሴት ዘፋኝ እንደሆነች አስመስክራለች::

ግን ይሄ ሁሉ የሞራል ድቀትና አደገኛ ግድየሌሽነት በሃገራችን የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ በተለይ በዘፋኞቻችን ላይ እንዴት ሊመጣ ቻለ? ኪነጥበባውያንስ ነፍሳቸው ምን ያህል ብትደነድን ነው ይሄንን ኑ  በቢራ ተደሰቱ  የሚል መአት ሲዲያቸው ላይ ለጥፈው ግዙን የሚሉት? መጠጥን ማስተዋወቅ ከስነ ጥበብና ትውልድን ከማስተማር ጋር ምን አያያዘው? ከሰፊው ህዝብ በፊት እንዲህ አይነት አካሄድ ለአገር ጥሩ እንዳልሆነ የሙዚቃ ሰዎቻችን እንዴት ማወቅ ተሳናቸው?

አቤት ጥያቄዎቼ ብዛታቸው በዚህ ጉዳይ ላይ ትንሽ ነገር መጻፍ አስቤያለሁ ያልኩት ወዳጄ ‘አንተ እኮ በጣም የምትገርም እውነቱን አልቀበልም ብለህ ዝም ብለህ የምትንገላወድ ምስኪን ፍጡር ነህ:: እዚ አገር ዘፋኙ እንዴት ሞራሉና ስብእናው ወርደ ትለኛለህ? የዚ አገር ዘፋኝ አይደለም እንዴ እየዘመረ አምባገነኑን መለስ ዜናዊን ነቢይ ነው ሲለን የነበረው? የዚ አገር ዘፋኝ አይደል እንዴ የማያቀውን ታሪክ አዋቂ ነኝ እያለ የሚዘላብደው? የዚ አገር ዘፋኝ አይደል እንዴ በመሃይምነቱ ዘሎ ፓርቲዎች አስታርቃለሁ የሚለን? የዚ አገር ዘፋኝ ሲጀመር ምን አይነት ሞራል እና ስብእና አለው እና ነው አሁን ሞራሉ ወደቀ ምናምን እያልክ የምትቀባጥረው? የበውቀቱ ስዩም እና የሌሎች ታላላቅ ደራስያን መጽሃፍ ምረቃ ላይ የማይገኙ ዘፋኞችና የኪነጥበብ ሰዎች አይደሉም እንዴ በሚኒስትሩ በረከት ስምኦን መጽሃፍ ምረቃ ምሽት እንግዳ ከበር ከመቀበል አንስቶ እስከ ዝግጅቱን መምራትና ማድመቅ ሲያሽቃብጡ የነበሩት? የዚ አገር ዘፋኝ እና የኪነጥበብ ሰዎች ያለ ምንም እውቀት የሚሰብኩን ሁሉ ስለ አባይ፣ ስለ ህዳሴ፣ ስለ ትራንስፎርሜሽን እና ስላለው የሃገሪቷ እድገት አይደለም እንዴ? የህዝብ መበደል፣ የኑሮ መወደድ፣ የህዝብ በህግ ጉዳይ ያላግባብ መንገላታት መቼ ተሰምቷቸው ያቃል እና ነው ዛሬ ሞራላቸው ወደቀ የምትለኝ? ‘ ብሎ በቁታ እየገነፈለ ተወኝ አለኝ:: ወድያው ደግሞ “ግን ደሞ” ብሎ ጀመረ “ግን ደሞ አንዳንድ በጣት የሚቆጠሩ ነፍሳቸውን ጊዜያቸውንና ሁለመናቸውን ለኪነ ጥበብ የሰዉ እንዳሉም የማላቅ አልምሰልህ እኔ እነዛን ጥቂቶችን እጅግ በጣም አከብራቸዋለሁ” ብሎኝ ሌላ ጨዋታ አውግተን ተለያየን:: እኔም ብዙ ማሰብ ጀምሬ አውጥቼና አውርጄ…..
Michael Belayeneh kuku
እውነትም ከዘፋኞች ሞራል ዝቅጠት ጀርባ የሚታይ ወይ አላዋቂነት ፣ ወይ ጥቅም እስካገኘሁ ምናገባኝ ማለት ፣  ወይ ደግሞ ትልቅ ድንቁርና አለ በሚለው ተስማማሁ:: እንደዚህ ያልኩበት ምክንያት ምንድነው? ነጥቦቼንም በዚህ መልኩ አስቀመጥኩ

  • ኮፒ ራይቱ አላሰራ አለን፣ ተቸግረናል፣ በጣም ተቸገርን፣  እየተዘረፍን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ መፍትሄ ይፈልግልን በማለት ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስቴር ጋር ስብሰባ ሲያደርጉ አምሽተው ተቸግረናል እየተዘረፍን ነው ባሉበት አፋቸው ዝግጅቱ ላይ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በስጦታ መልክ የወርቅ ብእር እንደሰጡዋቸው ሳስታውስ፣
  • ባደባባይ ሰው እንዲገደል ያደረገ መሪ ሲሞት ከተከበረው ብሄራዊ ቲያትር እስከ ቤተመንግስት ምነው ተለየኸን መስከረም ሳይጠባ የሚለውን ዘፈን እየዘፈኑ ነጠላ አደግድገው (ለቅርብ ዘመዶቻቸው የማያደርጉትን) እያለቀሱ መሄዳቸውን ሳስብ፣
  • ከእንግዲህ ሻማ ለልደት ነው እያሉ የማያቁትን የኢንጅነሪንግ ሙያ እየተጨማለቁበት ሳይ ከአንድ ግድብ ምረቃ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ የኤሌክትሪክ ችግር እንደማይኖር ማብራሪያና ዲስኩር የሰጡትን ሳስበው፣
  • ታላቅ የኦርቶዶክስ አማኝ ነኝ በማለት የማያቁትን የቤተ ክርስቲያንን ህግና ቀኖና ባልተከተለ መልኩ በድፍረት መዝሙር ዘምረው ማሪያም ማርያም የሚል ነጠላ ዜማ በለቀቁ ማግስት ዳንኪራና አስረሽ ምቺው ማድረጋቸውን ሳስበው፣
  • እንኳን ሌላ ሰው ያላግባብ ታሰረ ሊሉ እራሳቸው ያላግባብ ታስረው ያለ ወንጀሌ ነው የታሰርኩት በጣም ተበድያለሁ ለማለት ድፍረትና ብቃት የሌላቸው እንደሆኑ ሳስበው፣
  • ዘፈን እምቢ ሲላቸውና ከገበያ ሲወጡ በመሃይምነት እንዲሁም በከባድ ድፍረት ጌታ ጠርቶኝ ነው ብለው ለሃይማኖትም ለህዝብም ክብር ሳይሰጡ የስብከትንና የዝማሬን ተአምራዊ ጥበብ ምንም ሳይማሩ የፕሮተስታንት ዘማሪ ሲሆኑ ሳይ፣
  • እከሌ ሮጦ ሲያሸንፍ ሲዘፍኑ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ሲዘፍኑ ለአባይ ግድብ ሲዘፍኑ ሳውዲ ለሞቱት ሲዘፍኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሞቱ ሲዘፍኑ ጥበብን ከውስጣዊ ስሜታቸው ሳይሆን ከጊዜውና ከሰሞኑ ወሬ ጋር ሊወስዷት ሲፈልጉ ዜና የሚመስል ዘፈን አቅርበው ስሰማ፣
  • በመሃይምነትና በድንቁርና ታውረው ያልሰሩበትንና ያልለፉበትን የሌላ ሰው ዘፈንና ዜማ ከአገር ውስጥም ከውጭም ወስደው በማስረጃ ሲቀርብባቸው ይቅርታ በስህተት ባለማወቅ ነው እንደማለት ይህንን ፕሮግራም ይሰራ የነበረውን ለምን ይዋሻል ራዲዮ እስከማዘጋት መድረሳቸውን ስሰማና ሳይ፣

እነዚህንና ሌሎች ብዙ ያልዘረዘርኳቸውን ነጥቦች ካየን የኢትዮጵያ ኪነጥበብ በተለይ ሙዚቃ ከባለሙያ የእውቀት ማነስ ችግር የተነሳ ወርዶ በዚህ ባለንበት ዘመን እንኳን ራሱን መደገፍ እንዳቃተው ግልጽ ይሆንልናል:: ግን ዘፋኞቻችንና የኪነጥበብ ሰዎች ይህንን ችግር በጣም በሰለጠነ መንገድ ከመፍታት ይልቅ እራሳቸውን አዋርደው ያለቢራ ፋብሪካዎች ማስታወቅያ ካሴታቸውን ማሳተም ከማይችሉበት ደረጃ መድረሳቸውን በግልጽ የተናገሩ አይመስለኝም:: እንደውም ጥሩ ነገር በመስራት ያለብን ችግር ሊቀረፍ ይችላል ብለው ከማሰብ ከባለስልጣን ጋር፣ ከካድሬ ጋር፣ ከባለሃብት ጋር በመሞዳሞድ ሊያልፉ ያሰቡ ይመስለኛል:: ይህ ደግሞ በጣም አስነዋሪና ከኪነጥበብ ሰው ሳይሆን ከአየር በአየር ነጋዴ የሚመነጭ ተራ ውርደትና ስግብግብነት ነው::
Nesanet-Melese
ጊዜውን በውል ባላስታውሰውም በዚህ ሶስት አራት አመት ውስጥ የኢህአዴግ ባለስልጣኖች ያሳተሙትን የህዳሴ ዋዜማ የተሰኝውን DVD አባዝቶ በህገ ወጥ መንገድ ሲሽጥ የተያዘ ሰው 15 አመት እንደተፈረደበት ሰምተን ማንም እየተነሳ የድምጻዊያኖቻችንን ካሴት እና ሲዲ ለዘመናት በህገ ወጥ መንገድ ሲሸጥ ምንም አለመደረጉ ከዘፋኞቻችን በላይ እኔን ለምን እንዳስቆጨኝ አላውቅም::

የራሳቸውን መብት ሳያስጠብቁና ኮፒ ራይታቸውን ታግለው ሳያስከብሩ ዘፋኞቻችን ለኛና ለመጪው ትውልድ ያስባሉ ማለት ዘበት ነው ግን ቢሆንም ካለባቸው ችግር ለመውጣት የጀመሩት መንገድ ትክክል እንዳልሆነና ነገ ሁላችንም በልጆቻችን ፊት ሊያሳቅቀን የሚችል የሞራል ዝቅጠት መሆኑን ሳልጠቁም አላልፍም:: አርአያ የሚለው ቃል ለነገ ከማሰብና ለመጪው ትውልድ ከመጠንቀቅ ጋር አብሮ የሚሄድ ትርጉም ያለው ትልቅ ቃል ነው:: ይሄ ቃል ተረስቶ ወይ ደግሞ የሰው ስም ብቻ ሆኖ እንዳይቀር ካለኝ ስጋት ይቺን ጽፌያለሁ ደህና ሁኑ::

↧

በጎንደር ዳባት ሕጻን ሰለሞን ላይ ማን የጥይት እሩምታ አወረደበት?

$
0
0

Gonder
ከዳዊት ሰለሞን

ሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ ነዋሪ የነበሩት የ55 ዓመቱ አቶ ማስረሻ ጥላሁን የተመሰከረላቸው አርሶ አደር ገበሬ በመሆናቸው የክልሉ ግብርና ጽ/ቤት ሞዴል አርሶ አደር በማለት ሸልሟቸዋል፡፡የሁለት ወንድና የአምስት ሴት ልጆች አባት የሆኑት አቶ ማስረሻ ወሰኔን ገፍተሃል የሚል ክስ ቀርቦባቸው በዳባት ፍርድ ቤት 300 ብር መቀጮ ተጥሎባቸው በመክፈል ወደ እርሻቸው ቢመለሱም የገበሬ ቀበሌ ማህበሩ ሊያስቀምጣቸው አልቻለም፡፡

ጥቅምት 15/2006ዓ.ም ከሁለተኛ ልጃቸው ሰለሞን ማስረሻ ጋር አትክልት ተክለው አመሻሹ ለይ ተዳክመው መኖሪያ ቤታቸው ገብተዋል፡፡ማለዳ 12፡00 ከመኝታው ባላቋረጠው የውሾች ጩህት ከእንቅልፉ ተነሳው ሰለሞን በሩን ከፍቶ ሲወጣ የጥይት እሩምታ ይወርድበታል፡፡አባት ልጄን ብለው የሌሊት ልብሳቸውን እንደለበሱ ወደ ውጪ ሲወጡ የጥይቶቹ አቅጣጫ ወደ እርሳቸው በመዞሩ ማን እንደተኮሰባቸውና ማን እንደመታቸው ለማየት እንኳን ሳይታደሉ ይህችን ጨካኝ አለም ተሰናበቱ፡፡

መኖሪያ ቤቱ ላይ በሚወርደው የጥይት እሩምታ የተነሳ ሁለት ላሞችና አንዲት ጊደር ተገደሉ፡፡የስምንት አመቷ ስለእናት ማስረሻ ቀኝ እጇ ላይ በጥይት ተመታች፡፡ባለቤታቸውን በሞት የተነጠቁትና ምንም የማታውቀውን ህጻን ልጃቸውን አካለ ጎደሎ ያደረገባቸውን ጥይት ማን እንደተኮሰው ለማወቅ ለዳባት ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ አቤት ሲሉ ‹‹ባለቤትዎ ሽፍታ መረጃ ስለደረሰን ግድያውን የፈጸመው የጸረ ሽብር ግብር ሃይል ነው››ተብለዋል፡፡‹‹ሽፍታ እንዴት ባለ80 ቆርቆሮ ቤት ይሰራል?ልጆቹን ያስተምራል?ሞዴል አርሶ አደር ተብሎ ይሸለለማል?በየት አገር በብአዴን ስብሰባ ላይ እንድትገኝ ተብሎ በደብዳቤ ይጠራል?እንዴት ሽፍታ የመለስ ዜናዊን አደራ ለመወጣት በምንችልበት ሁኔታ ለመወያያት እንድንነጋገር ይባላል? ›› ጥያቄዎቹን ፖሊሶቹ ሊመልሱላቸው ባለመቻላቸው ወደ ክልሉ አስተዳደር አምርተዋል፡፡ክልሉ ለዞኑ ዞኑ ለወረዳው ደብዳቤ እየጻፈ እስካሁን ድረስ የአቶ ማስረሻ እውነተኛ የግድያ መንስኤ መታወቅ አልቻለም፡፡
999933_654015557990530_568853481_n
zemecha meles

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live