Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የህወሃት አፓርታይድ አገዛዝና የተቃዋሚ ኃይሎች !! (በጌታቸው)

$
0
0

በጌታቸው   

«ጅብ እንደ አገሩ ይጮሃል» እንዲሉ ዘፋኝ ስለሀገር ስለራሱ ውስጣዊ ስሜት ስለ ፍቅረኛው ስለቤተሰቡ ስለጓደኞቹና ስለሚታየው ወቅታዊና ነባራዊ ሁኔታ ይዘፍናል።ፖለቲከኛውም ስለ ወቅቱ ስለአለፈው የፖለቲካ ጉዳይ ስለሥልጣን ማጣትና ስልጣን መያዝ፤ ስለጨካኝ አገዛዝ ስለፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ይተርካል። ሁሉም እንደ ሙያውና አሰላለፉ ያለፈውንና የሚመጣውን ይተነብያል። እኔም ካለፈው የተመለከትኩትንና አሁን እጅ ላይ ያለውን ሁኔታ ስመለከት ወደ ፊት ምን ይመጣ ይሆን በማለት የራሴንና የሀገሬን የኢትዮጵያ ተስፋ  በሚመለከት ሀሳቤን ብሰነዝርስ ብየ አሰብኩ።

በአጭሩ ለማስቀመጥ በዘውዳዊ አገዛዝ የመጨረሻ ዘመን አካባቢ  በነበረው ቀርፋፋ የፖለቲካ አያያዝ ምክንያት ተሸፍነው ሊታለፉ የማይችሉ በርከት ያሉ የሀገር ችግሮች በአደባባይ ላይ መውጣታቸው የግድ ሆነና ንጉሠ ነገሥቱንና ካቢኔያቸውን ከሥልጣን ገበታ ጠራርጎ የሚጥለው ሕዝባዊ ንቅናቄ በ1966ዓ/ም ወርሃ የካቲት ከዳር እስከዳር አስተጋባ። አንዳንድ ድርጅቶች ከዚያ በፊት ተደራጅተን ነበር ይበሉ እንጅ የሕዝቡን ትግል አደራጅቶ የሚመራውና ወደሚፈለገው ግብ እንዲጓዝ ለማድረግ ባለመቻሉ አንዳቸውም የሕዝብ ጥያቄዎች ሳይመለሱ ያልታሰበ ኃይል ወደ ሥልጣን ገበታው ብቅ አለ።ገብቶንም ይሁን ሳይገባን የመጣውን አዲስ ገዥ መደብ ተቃወምን ደገፍን ሥልጣን ያማራቸው ደርግ ብቻውን ጠቅልሎ ይዞ አላካፍልም አለ በለስ ሳይቀናቸው ሲቀር ወደ አመፃዊ ትግል ገቡ አልተሳካም። ቀስ ብለው በጓዳ የገቡትም ወደ ደርጉ አዳራሽ ብቅ ቢሉና ሰነድ መሸጥ ቢጀምሩም ያችን ሥልጣን ደርግ ሊያቀምስ አልቻለም።ደርግ ግራ ተጋብቶ ነበር ቢባል ስህተት እንደማይሆን የሚያሳዩ ሁኔታዎች ነበሩ፦ ደርግን ወደ ሥልጣን ያመጣው የዝቅተኛው የወታደራዊ መኮንኖች ውስጣዊ ትግል ብቻ ሳይሆን በመላ ሀገሪቱ የተቀጣጠለው የሕዝብ አሻፈረኝ ባይነት ሆኖ ሳለ እነዚህን ጥያቄዎች ወደጎን በማድረግ ሥልጣኑን የማመቻቸት ትኩሳቱ ላይ ተጠመደ። ሌላው በሁሉም በር መግባት የሚቻልበት ቤት ሲገኝ የተነሳውን የተለያየ ምክንያት ያዘለና ተልዕኮ ያለውን ፖለቲካዊ ተቃውሞ ወይም ራሱን ደርግን ተቃውመው የተደራጁትን ድርጅቶች ጥያቄ በፖለቲካዊ አግባብ ሊፈታ ባለመቻሉ የተቃዋሚው ኃይል እየበረከተ ሄደ። የተቃዋሚ ኃይሎች በሦስት መስመር የተሰለፉ ሆነው አንዳንዴ እርስ በርሳቸው እየተባሉ ደርግ የተወሰነ እፎይታ ያግኝ እንጅ ከአካባቢ አገሮች ወረራ ጋር ተዳምሮ 17ቱ የደርግ የሥልጣን ዘመን ሕዝብን የሀገርን ኢኮኖሚ ያወደመና መጨረሻው የከፋ አወዳደቅ የወደቀ ደርግ ነበር። ሻእቢያ ለመገንጠል እንደ ነዳጅ የሚያገለግለውን ህወሃትን በማጠናከር አሳደገ ፤ ህወሃት ደግሞ በሻእቢያ ሰርጎ ገቦች እየታጀበ ከጌታው ሻእቢያ የሚወርድለትን ትእዛዝ ለማቀላጠፍና ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ታማኞችን በመመልመል ማደራጀቱን ቀጠለ።እንደሚታወቀው ኢህአፓ በኤርትራ ጉዳይ ግልጽ አቋም ሳይኖረው የዘለቀው በኢሳይያስ አፈወርቂ ማስፈራራት ብቻ አልነበረም።በራሱ በኢህአፓ ውስጥ የፖሊትና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትና የአመራሩን ሚና ይጫወቱ የነበሩት ኤርትራውያንና ትግራውያን እንደነበሩ ግልጽ ነው።አሁንም ኢህአፓ ነባር አባሎቹን አሰባስቦ የተወሰነ ድንጋይ እንኳን እንዳይወረውር ገትተው የያዙት እነዚሁ የኤርትራና ትግራይ ትውልድ ያላቸው የሻእቢያን ይሁን የህወሃትን ዓላማ ለማሳካት በስመ ታጋይ ኢህአፓ ውስጥ በመግባት ኢህአፓን የበተኑ የኢትዮጵያ አንድነት ሊንኮላሽና የመገንጠሉ ፍላጎት ግቡን ሊመታ የሚችለው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖትና አማራው ሲመቱ ነው በሚል ዓላማ ላይ አነጣጥረው የተነሱ እንደነበሩ መረጃ የሚያስፈልገው አይመስለኝም። ክፍሉ ታደሰ «ያትውልድ በሚል የጻፈውን ማንበብ ከቻላችሁ መረጃ አንድ ይኖራችኋል። መረጃ ሁለት የሪጅን ሦስት(የበለሳው ግንባር)ኢህአፓን ከድቶ ትግራይ ገብቶ በህወሃት ስር ሊወድቅና አሁን የደረሰውን «የቢሔራዊ ውርደት» እንዲሁም ጠቅላላ ሀገራዊ ቀውስ የፈጠረው የኢህዴንን ደባ መመልከት በቂ ነው። ኢህዴን ኢህአፓን እንዲበተን አስተዋጽኦ ማድረጉ ብቻ ሳይሆን 1/የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ኦህዴድን)፤ 2/ድሮ የስምጥ ሸለቆ አሁን የደቡብ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት(ደሕዴድ)ና 3/የወታደራዊ መኮንኖች ድርጅት ተብሎ የተደራጀና ቶሎ ብለው ያፈረሱትን የጌታውን የህወሃት ዱላ ፈርቶ እነዚህን ድርጅቶች ለማቋቋም በቤት ሥራ ተጠምዶ ከዚህ ያደረሰ ስንኩልና ቅጥረኛ ድርጅት ሲሆን አሁን ደግሞ (ብአዴን)ብሔራዊ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ በማለት ሰፊውን የአማራ ሕዝብ አፍነው የሚገዙ ትውልደ ኤርትራና ትግራይ የሆኑ የአማራውን ሕዝብ ለስደት፤ድህነትና እልቂት ዳርገውት ይገኛሉ።ሰፊው የአማራ ሕዝብ የሌላውን ዛር እየተላበሰ ግንባር ቀደም ለሀገሩ ድንበር መከበር መስዕዋትነት ከመክፈሉ ያለፈ የየትኛውም ሥርዓት ተጠቃሚ እንዳልነበረ በጠላትነት ፈርጀው መጠነ ሰፊ ጥቃት የሰነዘሩበት ድርጅቶች ጠንቅቀው ያውቁታል።ነገር ግን ፀረ ህዝብ ዓላማቸውን ለማሳካት እንዳይችሉ ቀድሞ የሚነሳውና በግንባር ቀደምትነት የሚፋለማቸው ስለሆነ እንፍጀውን አውጀውበታል እየፈጁትም ነው።ለምሳሌ ከአማራው ነገድ ሕዝብ የበቀለው አንዱዓለም አራጌ አንዲት ቅንጣት ታክል ስህተት ፈጽሞ አይደለም የእድሜ ልክ ጽኑ እስራት የተፈረደበት አንዱዓለም እውነት ነው የተናገረውም እውነትን ነው። እውነትን ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ባለመዋሸቱ ታስሯል።ግድ የለም ይታሰር ነገ ይፈታል።ዳሩ ግን በዓለም ከፍ ያለ ዝና ያተረፈችውን ኢትዮጵያ ሀገራችን ለማዋረድ ፤ለመበተን ፤ሀብቷን ለመዝረፍ ትውልዷን ማምከን እንዴት ተወሰነ? በሳውዝ አፍሪካ የተካሄደውን የነጮች በጥቁር ላይ ለዚያውም በራሳቸው ሀገር የአፓርታይድ አገዛዝ «በዓለም ደረጃ ታላቅ ዝና ያተረፉት የነጻነት አርበኛ ኔክሰን ማንዴላን ዜና ረፍት» ምክንያት በማድረግ ዓለም አቀፍ ሜዲያዎች በምስል እያስደገፉ ያቀረቡትን የክቡሩን ሰው የሕይወት ታሪክ ስመለከት በሀገራችን ዜግነታቸው ኢትዮጵያዊ የሆኑ መንፈሳዊና ብሔራዊ ሞራል የሌላቸው ሀሳበ ኩድኩድና ድኻዎች(ጥቁር ጣሊያኖች )በራሳቸው ሕዝብ ላይ የሚያደርሱትን ልክ የለሽ ጨካኝና አረመኔያዊ አገዛዝ ከሳውዝ አፍሪካው ጋር እንዳነጻጽረው ገፋፋኝና ወደ ተነሳሁበት ነጥብ ተመልሸ አሁን የመንግሥታዊ መዋቅሩን የያዘውና በጫካ ሕግ እየገዛ ያለውን ድርጅት ሁለት ካዝና ያለው ተቋም በሚመለከት ጊዜየን ሳላባክን በመደምደም ወደ የተቃዋሚ ኃይሎች በመጠኑ የሚሰማኝን ለማካፈል የሚከተለውን ማስነበብ እወዳለሁ።

ህወሃትን ፦ 1/መንግሥት ማለት አልችልም 2/ ወያኔም አልልም(ኢህአዴግም)ማለት አልችልም መሆን የሚችልበት ወይም በዚህ ስም ለመጥራት አንዱንም ነጥብ ወይም መስፈርት አሟልቶ ስለማይገኝ። ወያኔ የሚለው ከግእዙ ትርጓሜ ሲወሰድ አበየ-አመጸ- እምብኝ አለ ስለሚል ማንም የሚጠቀምበት እንጅ በቅጥረኝነት ለተሰለፈ ቡድን መጠሪያ አይሆንም። ምናልባት የአቶ ተክሌ የሻው የትግራይ ወያኔዎች የሚለው ይመቸኛል።መንግሥት ለማለት የሚከብድበት ምክንያት ይህ ቡድን ተግባሩ የማፊያ እንጅ መንግሥታዊ ባህሪ የለውም በዚህ ቡድን ውስጥ የተሰባሰቡትን ስንመለከትም እዚህ ግቡ የባይባሉ ስነምግባር የሌላቸውና በደም የሰከሩ ሰሞነኞች ስለሆኑ በተለመደው ህወሃት እያልኩ እጠራቸዋለሁ።ኢህአዴግ ለማለት ደግሞ አይቻልም ግንባሩ ወይም ስብስቡ ህወሃት ቁጭ ብድግ ሲያስብለው ቁጭ ብድግ የሚልን ስብስብ ግንባር ብሎ ቢጠራውም በዚህ ስሙ መጥራት አግባብ ሊኖረው አይችልም።

ህወሃት ዘራፊ ድርጅት ነው። በተለያዩ ስሞች እየተጠራ ከዚህ የደረሰው ህወሃት ኢትዮጵያንና አማራን ማጥፋት ብሎ ከተነሳበት ጊዜ ጀምሮ የግል፤ የድርጅትና የመንግሥት ተቋሞችን በመዝረፍ የተሰማራ ለመሆኑ አሁንም በዚሁ መንገድ መቀጠሉን ራሱ ተቋሙ ሳያፍር የሚገልፀው ጉዳይ ስለሆነ በዚህ እንተማመንና የሀገር የሆኑ ታላላቅ ተቋሞችን ለትውልድ እንዳይተላለፉ ማውደም ድልድዮችን ግንቦችን ታሪካዊ ቅርሶችን ማፈራረስ ለምሳሌ የዋልድባ ገዳም የመሰሉትን በዶዘር ገብቶ ማረስ ከአንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ የማይጠበቅ ምግባረ ብልሹ የሆነ ተግባር ነው። የመንግሥት መዋቅርን የተቆጣጠረ ድርጅት አሁንም በዚያ መጥፎና የትግራይን ሕዝብ አልፎ ለሌላውም እልቂት ምክንያት የሆነውን የደደቢቱን ስሙ አለመቀየሩ፤ የገብረሕዮት አክሲዮን ወጋገን ባንክ፤ ጉና የንግድ ድርጅት፤ኤፈርት፤የምናምንቴ ትራንስፖርት …ወዘተ ብሎ የሚጠራቸው ተቋማቅት  የመዝረፊያ ተቋሞች ናቸው።በነዚህ ተቋሞች አማካኝነት የሚዘረፈው የሀገር ሀብት ለሀገር እድገት የሚውል አይደለም።አንድ ምሳሌ እንውሰድና እንመልከት የህወሃቱ ጉና የንግድ ድርጅት ማሽላ ፤ሰሊጥና ጥጥ ይገዛል እንበል የሀገር ባለሀብቶችም እንዲሁ ማሽላ ፤ ሰሊጥና ጥጥ ይገዛሉ።ነገር ግን ይህ የግዥ ወቅት ከመድረሱ በፊት ከላይ እስከ ታች ባለው የህወሃት መዋቅር መመሪያ ተላልፎ ካድሬው የግል ባለሀብቶችን በትዕዛዝ በማገድ ጉና የንግድ ድርጅት ያለ ተወዳዳሪ በሚፈልገው ዋጋ ምርቱን የሚገዛበት ሁኔታ ይመቻቻል።በሥራው የሚሳተፉትም የድርጅቱ አባላት ብቻ ናቸው።ይህ አይነቱ የንግድ ድርጅት በተመሳሳይ በአማራ ክልል አምባሰል ሲኖር በደቡብና በኦሮሞ ክልልም ለጊዜው ስማቸውን ባልይዘውም በዚህ መንገድ በንግድ ሥራ የተደራጁ ተቋሞች አሉ።የሕዝብና የጭነት ማመላለሻ አገልግሎ፤ባንኮች፤በመካናይዝድ የሚያርሱ የእርሻ ድርጅቶች፤በሕዝብ ስም ለድርጅቱ ከውጭና ከሀገር ውስጥ እርዳታ የሚሰበስቡ እንደ ጥረትና ኤፈርት እንደ አልማ የመሰሉ የልማት ማህበር የሚባሉ ሕዝብን ያደኸዩ የመዝረፊያ ተቋሞች ሀገሪቱን ከጫፍ እስከ ጫፍ ጥፍረው ይዘው የሀገር ሀብት ይዘርፋሉ።የሚገርመው ነገር እነዚህ ተቋሞች ከፍተኛ ካፒታል ያላቸው ሲሆን ለሀገር እድገትና ግንባታ የሚውል «የገቢ ግብርና ታክስ የማይከፍሉ »መሆኑና ተዘርፎም ይሁን ተነግዶ የተገኘው ገንዘብ ጥቂቶች ተከፋፍለው የሚጠቀሙበት መሆኑ ነው።»

ህወሃት፦መሞት የሚፈልግ ነገር ግን የሚገድለው ያጣ ድርጅት ነው።ይህ ድርጅት ሥልጣን ከያዘበት ቀን ጀምሮ በኃይል የሚተማመንና ጦር በማደራጀት ሕዝቡን አስገድዶ ለመግዛት ወይም በብጥብጥ ሀገር እያመሰ ለመኖር ያሰበ መሪዎቹ በደም የሰከሩና በውስጣቸው ሰላምን ያጡ ሲባንኑ የሚኖሩ ለመሆናቸው እያንዳንዷን የወንጀል ድርጊት አፈጻጸም ወስደን ብንመለከት ያን ተግባር ለመፈጸም የሚያስገድደው ምክንያት ከሕዝብ የተነጠለ ተስፋ ያጣ በውስጡ መተማመን የሌለውና ለመስንበት ሲባል ተመሳሳይ በወንጀል ተግባር የተጨማለቁ ኃላፊዎች ያሉበት ሲሆን ለጥቅሙ ሲል የታጠቀውን የመከላከያ ኃይል ተማምነው የሚኖሩ ናቸው።ለዚህም ነው በመከላከያ ሠራዊቱ ውስጥ በየጊዜው የመቀያየር በጡረታና በመሳሰሉት ምክንያቶች ማግለል ኦሮሞውንና አማራውንም በጥርጣሬ ማየት ማሰርና ማባረር የሚስተዋለው

ሀወሃት፦አንድነትን አጥብቆ የሚጠላ በዘረኝነት የተበከለ ድርጅት ነው።አንድ ለአምስት አደረጃጀትን መነሻ አድርገን ብንወስድና 99.6 ድምጽ አግኝቼ ተመርጫለሁ የሚለው ኃይል ውሸቱን እንዴት እንደሚፈበርከው በግልጽ ያሳያል።99.6 ድምጽ ያገኘ ድርጅት በህዝብ ዘንድ ተአማኒነት ያገኘ ማለት ነው።አንድ ለአምስት ማለት ደግሞ ከሕዝብ የተነጠለና ሕዝቡን የማያምን የሕዝቡን የየእለት ከእለት እንቅስቃሴን ለመከታተል አንድ ሰው አራቱን በመከታተል ሪፖርት የሚያደርግበት መንገድ ነው ሁለት በጣም የማይቀራረቡና የሚጋጩ ሁኔታዎች። ስለዚህ ድርጅቱ የሕዝብ ድምጽ ሌባ መሆኑን ራሱ የተቀበለ ለመሆኑ ይሰመርበታል።በሀገር ውስጥም ይሁን በውጭ ሀገር ህወሃት በርከት ያለ ገንዘብ በመመደብ እንደ ሽመልስ ከማል የመሰሉ አፈጮሌዎችንና ጮማ ምላስሞችን በማሰማራት የእቁብ ፤ የእድር ፤የሰንበቴ፤የሚካኤል የጊዮርጊስ ወዘተ… እና የመረዳጃ ፤የልማት ማህበራትን ፤ድርጅቶችን፤በቤተክርስቲያትን  በተቃዋሚ ኃይሎች ውስጥ፤በእስልምና ሃይማኖትና በማንኛውም የሕዝብ ስብስብ ውስጥ በመግባት የተጋቡ የአማራ ወንድና የትግሬ ሴትን እስከ ማፋታት የሚሄድ የስለላ መዋቅር ያለው ፀረ-ሕዝብ ድርጅት ሲሆን ዛሬ ሌላ ነገ ሌላ የሚቀላብደው በችግር ውስጥ የሚገኝ ጸረ-ሰላም በመሆኑ ነው።

ህወሃት፦ህወሃት መንፈሳዊ ሞራል  ብሔራዊ ወኔ የሌለው ቅጥረኛ ድርጅት ነው።በኢትዮጵያ የተለያየ እምነት የሚከትሉ እስልምና እና ክርስትና እምነታቸው የሆኑ ለረጅም ጊዜ በመከባበርና በመተባበር ሲኖሩ ይህ ድርጅት ደርግን ከተካበት ቀን ጀምሮ ሌት ከቀን አንዱን በአንዱ ላይ ለማናከስ ያልፈነቀለው ድንጋይ የለም።ሊሳካለት ግን አልቻለም።የቻለው ወይም የተሳካለት ቢኖር የእስልምና ሃይማኖት መሪዎቹን ማሰር ካድሬ እስላሞችን በመሪነት መሾምና የሀገር ቤቱን ሲኖዶስ ደግሞ ህወሃታዊ ሲኖዶስ እንዲሆን ማድረግ ነው።ዛሬ በውጭ ቀላልና ዋና የገቢ ምንጭ ሆኖ የሚገኘው ህወሃት በቀጥታ ወደ ውጭ የሚልካቸውን የሰንበት ተማሪዎችን ከመንፈሳዊ ኮሌጅ የለቀቁና ካድሬዎቹን ካባ እያለበሰ ቄስ ናቸው በማለት የአማራ ፤የኦሮሞ፤የትግሬ የሌላም የሌላም ቤተክርስቲያን በየመንደሩ በመክፈት ሕዝቡን ማራራቅና ቅሬኔ ውስጥ ማስገባትን ዋና ተግባሩ አድርጎ ይዞታል፤በወርሃዊ መዋጮና በሙዳይ ገንዘብ ሀብታም የቤተክርስቲያን መሪ መፍጠርና የማይሰሩ የሰበካ ጉባኤዎችን በማስመረጥ የህወሃትን መዋቅር ማጠናከር አንዱ ስልት ሆኗል።የሚገርመው ግን ጽላቱ የት እንደሚገኝ ነው።አንዳንዱ ከግሪክ ነው ይላል ሌላው ከኢትዮጵያ ነው ይላል።ሞቀም ፈላም ተጠያቂው ግን አስፈጻሚው ህወሃት ይሆናል ማለት ነው።በሌላው መልኩ ህወሃትን ስንመለከት ትግራይን ገንጥሎ ከኤርትራ ከአፋር ከአማራ ሰሜን ወሎና ሰሜን ጎንደርን ቆርሶ በመውሰድ ታላቋን የትግራይ ሪፐብሊክ መመስረት እንደነበርና አሁንም ሕዝባዊ ኃይሉ እየገፋ ከሄደ የኢሳይያስን ቡድን ገፍቶ የሚጥል ሴራ በመሸረብ ኢትዮጵያና ኤርትራ የሚኖሩ ኤርትራውያን በበላይነት የሚመሩት መንግሥት ለመመሥረት የማይቦዝን ሲሆን የአሰብን ወደብ አልቀበልም ያለበት ምክንያትም በኤርትራ እጅ እንዲቆይ ማድረግ ከዚህ አንፃር ሊታይ የሚችል መሆኑ፤ ኤርትራን ያስገነጠለበት አጀንዳም ባካፕ ወይም የኋላ ደጀን በማድረግ ኢትዮጵያን እስከሚያፈራርሱ ጊዜ ለመግዛት ሊጠቀሙ የሄዱበት መንገድ መሆኑን እኛ ኢትዮጵያ ሀገራችን የምንል ጉዳዩን ከተለያየ አንግል ለጥጠን ልናይ ይገባናል፤ የኢትዮጵያን ለም መሬት ኢትዮጵያውያንን በማፈናቀል ለውጭ ከበርቴዎች በነፃ የቸረ፤ ሰፊና ለም መሬት ከኢትዮጵያ ሳልፎ ለሱዳን የሰጠ የኢትዮጵያን ዳርድንበርና ሉዓላዊነት ያስደፈረ ከሃዲ ድርጅት ነው።በነዚህና በመሳሰሉት ምክንያቶች ህወሃት አንድም ቀን ቢሆን ማደር የማይገባው በሞት አፋፍ ላይ ሆኖ ኑና ግጠሙኝ በማለት ጉድጓዱን ቆፍሮ ቀባሪ እየጠበቀ አጥፍቶ ሊጠፋ የተዘጋጀና እንደ እንሰሳ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ያለ ጀግና በሀገር ጠፍቶ 22ኛውን ዓመት አሳልፎ 23ኛውን አመት እየተሻገረ ያለ ሀገርን ያጠፋ የዐረብና የምዕራባውያን ጉዳይ አስፈጻሚ ቅጥረኛ ድርጅት ነው።

በመጨረሻም ህወሃት መሬት ለሱዳን መስጠት ለምን ተገደደ የሚለውን ስንመለከት 1ኛ/ ሱዳን ለህወሃት ሆነ ለሻእብያ ትልቅ ባለውለታ ነች ወይም አሁንም ሆነ በደርግ ወቅት ከደደቢት የበለጠ ምሽግ ሆና ማገልገሏ ግልጽ ነው።2ኛ/ ህወሃትን የሚቃወሙ ኢትዮጵያዊ ድርጅቶችን በሱዳን አማካኝነት ከሱዳን ምድር ጽ/ቤታቸው እንዲዘጋ ንብረታቸው እንዲበረበር፤ከሱዳን እንዲወጡ በማድረግ የሱዳን መንግሥት ከፍተኛውን ድርሻ ተወጥቷል።ለዚህም ነው የመሬት ጉርሻ ለሱዳን እንዲሰጡ የተገደዱበት ይኸም ቀደም ሲል ቃል የተገባበት እንደሆነ ሳይታለም የተፈታ ነው። የሚገርመው ግን ከኔ ከራሴ ጀምሮ የሱዳንና የኢትዮጵያን ድንበር አበጥሮ የማያውቅ ይኖራል ብየ አላስብም ራሱ ህወሃት ያውቀዋል።የህወሃት ዓላማ ግን ሱዳን ከኢትዮጵያ የወሰደችውን መሬት ልትጠቀምበት ትችላለች ብለው አምነውበት ሳይሆን በሁለቱ አገር ሕዝቦች መካከል የሚኖረውን የወንድማማችነትና የወዳጅነት ግንኙነት ለማደፍረስ የታሰበ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱ እንዲሻክርና እንዳይኖር በብጥብጥ ለማኖር የተጠመደ ፈንጅ ነው።

ወደ የተቃዋሚ ኃይሎች ስመጣ የተቃዋሚ ኃይሎችን በሁለት ከፍየ አያቸዋለሁ፦

1ኛ/ ሥርዓቱን በሰላማዊ መንገድ በመታገል በዴሞክራሲያዊ ምርጫ አሸንፈን የህግ የበላይነት የተረጋገጠበት፤ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጎች በእኩልነት ተከባብረው እንዲኖሩ የሚያደርግ ዴሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ሥርዓት ለመገንባት የተነሱ ናቸው። መነሻቸው ወይም ዓላማቸው በጣም የሚደገፍና ቅን አስተሳሰብ ነው። ችግሮች ድርጅቶች ህወሃትን በሚገባ አውቀው እንደ ባህሪው ክፋት ተንኮሎችን በጣጥሶ መሄድ የሚያስችለውን መንገድ አልተጠቀሙበትም። ይኸውም መጀመሪያ አንድ ጠንካራ ሕብረ ብሔራዊ ድርጅት መገንባት አለመቻላቸው ሲሆን ሁለተኛ የተንበሸበሸ ብዛት ሳይሆን ጥራት ያላቸው ጥቂት ድርጅቶች ቢኖሩ መልካም ነበር።ይህም አልሆነም ባሉበት ደረጃም ሆነው ገና ከመጀመሪያው መደራጀትን ሲመርጡ ህወሃት ሰርጎ እንዳይገባ የተጠነቀቁ አይደሉም።ይህ በሀገር ቤት ይሁን በውጭ አገር ያሉትን የሚያጠቃልል ነው።ይህን ለማለት ያስገደደኝ የህወሃትን ጠብ አጫሪነትና ሰርጎ ገብነት በተለያዩ ደረጃዎች በመመልከቴ በድርጅቶች ውስጥ የሚፈጠሩትን የመከፋፈልና የሚያጋጥሙ ችግሮችን ተገንዝቦ አስፈላጊውን መፍትሄ መስጠት ባለመቻላቸው የህውሃት እጅ ገብቶበታል እንድል ያስገድደኛል። በሕቡ አደረጃጀት ምን ያህል ርቀው እንደሄዱ ባላውቅም አንድ ለአምስት የተደራጀ የስለላ መዋቅር ዘርግቶ የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ የልብ ትርታ አዳምጣለሁ ብሎ የሀገር ሀብት ዘርፎ የተደራጀን ቡድን መሰናክል ለመበጠስ ሕቡ አደረጃጀት አስፈላጊ በመሆኑ ነው። ሁሉም ድርጅቶች ፕሮግራማቸውን ለህዝብ ለማስተዋወቅ ፤ አባልና ደጋፊ ለማፍራት ያጋጠማቸውን የካድሬ ፤ የደህንነት፤ የመከላከያና የፖሊስ ወከባ ሁላችንም ሳንገነዘበው አልቀረንም ለዚህ ችግር ሕቡ አደረጃጀት አስፈላጊ ነው ብየ አስባለሁ። በተረፈ አንድነት ሊፈጥሩ አለመቻላቸውና በተናጠል ትግሉን ለመቀጠል የሚሄዱበትን መንገድ እርስ በራሳቸው የሚያደርጉትን መጠላለፍ ሳልደግፍ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ በህዝብ ላይ የሚደርሰውን ግድያ፤ እስራትና አፈና ፤ ድብደባ ፤የንብረት ዘረፋ፤ማፈናቀል…ወዘተ ለህዝብ ጀሮ እንዲደርስ በማድረግ የሚሄዱበት መንገድ ጎሽ የሚያስብል ሆኖ አግኝቼዋለሁ ቀጥሉበት ።

2ኛ/ ህወሃትን በቋንቋው እናናግረዋለን እንጅ በሰላማዊ ትግል ሥልጣን ሊያስረክብ አይችልም ብለው በትጥቅ ህወሃትን ለማንበርከክ የተሰለፉ የተቃዋሚ ኃይሎችን ሞራል በእጅጉ እያደነቅሁ ነገር ግን እነዚህ ኃይሎችም ቢሆን ከፍ ብየ እንደገለጽኩት ከህወሃት ሰርጎ ገብነት ነፃ ለመሆናቸው፤ እርስ በርስ ከመጠላለፍ የወጡ ለመሆናቸውና በጋራ አንድ ግንባር ፈጥረው ለመታገል ያላቸውን እምነትና ቁርጠኝነት ለማመን እርግጠኛ አይደለሁም። አንዳንዶቹ ከተመሠረቱ ህወሃት በጥቂት ዓመታት የሚበልጣቸው ሲሆን ቀደም ብለው የትጥቅ ትግሉን የጀመሩ ሲሆን በነዚህ ኃይሎች ነፃ የወጣ ምድር አለ ሲባል ሰምቼ አላውቅም። ምናልባት ለድርጅታዊ ጠቀሜታና ደህንነት ተብሎ ከሆነ መልካም ነው። አንዳንዶቹ ማፈግፈጊያ ያደረጉት የኤርትራን ምድር ሲሆን በበኩሌ ይህ የግሌ አስተያየት ነው የኢሳይያስን መንግሥት በማመንና ከሱ ድጋፍ በማግኘት ህወሃትን ታግየ እጥላለሁ ብሎ ማሰብ« ከእባብ እንቁላል እርግብ ይፈለፈላል »ብሎ እንደማሰብ ነው ብየ አስባለሁ። ለምን ቢባል ወደ ኋላ እንመለስና ኢሳይያስ አፈርቂ በኢትዮጵያ ላይ ያለው አመለካከት ከዚያ በፊት በታጋይ ድርጅቶች ላይ ከህወሃት ጎን በመሆን ያደረገው ጭፍጨፋና የነበረው አቋም ሲታይ ጊዜን ማባከን ወይም በህወሃት መንገድ እየሄዱ ነው የሚመስለው። ሻእብያ ህወሃትን ቃል አስገብቶ እንደፈረስ ይጋልበው እንደነበር መዘንጋት የለብንም። ለምሳሌ ምን ያህል እርግጠኛ እንደሆነ ሙሴን ባላምነውም ሰበር ዜና በማለት ያቀረበውን ስንመለከት የኤርትራና ህወሃት ጀኔራሎችና ባለሥልጣናት በሳውዲዓረቢያ ስብሰባ ማካሄዳቸው ተግልጿል። በዚህ ከተግባቡ ምናልባት ኢሳይያስን በማስወገድ አፍቃሪ ህወሃት ኃይል በኤርታራ አደራጅቶ ትግራይና ኤርትራን በጋራ በማድረግ እንዲሁም ከአፋርና አማራ ክልል በእቅድ የተቀመጠውን መሬት አካሎ የመለስ ዜናዊ «ራእይ»ን ተግባራዊ ለማድረግ ከመሆን ሊያልፍ ይችላል ወይ? ይህ ከሆነስ የኤርትራን ምድር ደጀን ያደረጉ በትጥቅ ትግል የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች እጣ ፈንታ ምን ሊሆን ይችላል? በበኩሌ ነፍጥ ያነሱ ኃይሎች መጀመሪያ ሳይረፍድ ግንባር መፍጠር አለባቸው።ሁለተኛ የተከፈለው ይከፈል የኤርትራን ምድር ለቀው ኢትዮጵያ   ውስጥ ነጻ መሬት መያዝ ወይም የጎሬላ እንቅስቃሴ ሊያደርጉ ግድ ይላቸዋል። ከዚህ ባለፈ ግን አማራጩ የራሳቸው ቢሆንም በአፈና ላይ ለሚገኘው ሕዝብ ደርሶ ከአፈና ለማውጣት ጊዜ የሚገድል ሆኖ ነው የሚታየኝ። ከፍ ብየ እንደገለጽኩት ህወሃት ጥጋቡ መረን በመዝለሉ ሞትን እየናፈቀ ያለ የሰላማዊ ትግልን በር እንዳይከፈት አጥብቆ የዘጋ ተቃዋሚዎችን ትንሽም ቅንጣት ያህል ሊያከብርና በሀገር ጉዳይ በጋራ ሊመክር የማይችል እብሪተኛ ድርጅት በመሆኑ በትጥቅ ትግል ማስተንፈስ ከተቻለ ልክ የማይገባበት ምክንያት አይኖርምና ለሀገርና ለህዝብ ብላችሁ ትግስት አስጨራሹን የትግል ጎዳና ከጀመራችሁ በውጭ የሚገኘው ኢትዮጵያዊ ወገናችሁ ሕዝቡንና ሀገሩን ስለሚወድ የተቻለውን ሁሉ ድጋፉን እንደማይነፍጋችሁ እርግጠኛ ሆኘ ልነግራችሁ  እወዳለሁ። የተቻለውም በድጋፍ ብቻ ሳይገታ ትግሉንም ሊቀላቀል እንደሚችል ተስፋ አደርጋለሁ።

ለዛሬ ያለኝን በዚህ ጨርሻለሁ በቼር ይግጠመን።

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላአለም ትኑር!!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!

ሞት ለህወሃት!!!

 

ጌታቸው   Pen

 


አቶ አያሌው ጎበዜም የድል አጥቢያ አርበኛ እንደ ውሃ ላይ ኩበት እመሀል ላይ እንደዋለሉ የማይቀረውን ስንብታቸውን ተሰናበተዋል

$
0
0

ዳዊት መላኩ(ከጀርመን)

አያሌው ጎበዜ

አያሌው ጎበዜ

አቶ አያሌው ጎበዜም እንደምንም  የመምህርነት ስራቸውን ትተው የድል አጥቢያ አርበኛ በመሆን ገብተው ወይ ራሳቸውን ነፃ ሳያወጡ ወይ ህዝቡን በትክክል ሳያገለገሉ እንዲሁ እንደ ውሃ ላይ ኩበት  እመሀል ላይ እንደዋለሉ የማይቀረውን ስንብታቸውን ተሰናበተዋል፡፡ወያኔ እንደ ሸንኮራ ምጥጥ አድርጎ ተፋቸው፡፡እኔ እስከማውቃቸው አቶ አያሌው ከሌሎች የወያኔ ባለስልጣናት የሚለዮት በሙስና አለመጠርጠራቸው፤ብዙ ማውራት የማይወዱ ሲናገሩም ከባህል እና ከሞራል የማያፈነግጡ፤ለሚኖሩበት ማሀበረሰብ ክብር በመስጠት ሚስታቸው ሳይቀር አብረዋቸው ከሚኖሩት እድርተኞች እኩል መሳተፋቸው ነው፡፡ አቶ አያሌው እንደአባዱላ ገመዳ ብዙ ቤት ገንብተው ለትግሉ ስላስቸገረኝ ውሰዱልኝ ሲሉ አልተደመጡም፡፡እስካሁን ባለኝ መረጃ መሰረት አቶ አያሌው ባህርዳር ከተማ ውስጥ ቀበሌ 14 አካባቢ በማህበር ተደራጅተው በወሰዱት አንድ ቦታ ቤት እንደገነቡ ነው ፡፡ ዘመድ አዝማዳቸውን ስራ በማስገባት አይታሙም ፡፡የአቶ አያሌው ልጆች እንደ ሌሎች የባለስልጣን ልጆች አሜሪካ እና አውሮፓ ወይም አዲስ አበባ ውስጥ ባሉ ውድ የግል ትምህርት ቤቶች አይደለም  የሚማሩት፡፡እንደማንኛውም ደሃ ቤተሰብ ባህርዳር ውስጥ ባሉ የመንግስት ትምህርቤቶች ያስተምሩ ነበር፡፡

አቶ አያሌው እንግዲህ እነዚህ መልካም ነገር ቢኖራቸውም የተሰጣቸውን መክሊት አባክነው የክልሉ ህዝብ በየቦታው ሲፈናቀል የክልሉ መሬት እንደዳቦ እየተሸነሸነ ሲታደል የተቀመጡባትን ወንበር ላለማጣት በዝምታ ማለፍን መርጠዋል፡፡ይህ ደግሞ በምንም መልኩ ከተጠያቂነት አያድንም፡፡ከሌባ ጋር አብሮ ስርቆት ሂዶ  በቅርብ ርቀት ሲሰርቁ እያዩ ዝም ማለት እና የሰረቀው አብሮኝ ያለው ሰው ነው አንጂ እኔ ነፃ ነኝ ቢሉ ከቅጣት አያመልጡም፡፡እንግዲህ እርሳቸው በስልጣን ላይ በቀዮበት ጊዜ ለጠፋው ሀይወት፤ለወደመው ንብረት፤ለተፈጠረው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ድቀት የድርሻቸውን ይወስዳሉ፡፡

መቼም በዘመኔ ወያኔ ስራና ሰራተኛ ተገናኝተው ባይውቁም እንደአማራ ክልል  ባለስልጣናት በእውቀት ድርቅ የተጠቃ የለም፡፡”ሰው ሢታጣ ይመለመላል ጎባጣ” ነው ነገሩ፡፡ሰው ሲታጣ ማለቴ ለወያኔ በታማኝነት የሚያገለግል ማለቴ ነው፡፡አቶ አያሌውን የተኩት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በርቀት ትምህርት በማኔጅመት የመጀመሪያ ዲግሪ ሲኖራቸው በ1998 ዓ.ም የብአዴን ቢሮ ውስጥ ይሰሩ ነበር፡፡የተኛው የተምህርት ዝግጅት ተዛምዶ የክልሉየግብርና ቢሮ ኃላፊ ሁነው እንዲሰሩ እንዳበቃቸው የሚያውቀው ወያኔ ብቻ ነው፡፡ይባስ ብሎ ክልሉን የመምራት ሀላፊነት ለሳቸው መስጠት ከምጡ ወደ ዳጡ ነው፡፡ አቶ ገዱን የአማራ ወጣቶች ከከፍተኛ ትምህርቶች ተመርቀው የፓሪቲ አባል ካልሆኑ ስራ እንዳይሰጣቸው በክልሉ ላሉ ሁሉም ዞኖች ትእዛዝ ሲያስተላልፉ በተቃራኒው አባል ለሆኑት ስልክ ብቻ በመደወል እንዲቀበሉዋቸው ያል ምንም ውድድር እና ማስታወቂ  በደብዳቤ ብቻ ሲመድቡ እንደነበር ይታወቃል፡፡በተለይ በ1998ዓ.ም የንግድ እና ኢንዱስትሪ ጽ/ቤት በወረዳዎች መከፈትን ተከትሎ በሁሉም ወረዳዎች የተመደቡ ፈላፊዎች በዚህ አይነት የተመደቡ ነበሩ፡፡አቶ ገዱ የክልል ፕሬዚዳንት ቀርቶ ለቀበሌ አመራርነት ሚያበቃ ስብእና እንደሌላቸው ሚያወቁዋቸው ሁሉ የሚስማሙበት ሀቅ ነው፡፡ግን ምን ይደረግ ወያኔ በሚመራው ሀገር ውስጥ ለሀገር የሚጠቅም ነገር በነፃነት መስራት ስለማይቻል አንዴ አዲሱ ለገሰ፤አንዴ ደመቀ መኮነን፤አንዴ ገዱ አንዳርጋቸው እተፈራረቁ በህዝቡ ትክሻ ላይ ያለከልካይ ይጫናሉ፡፡

በመጽሀፍ ቅዱስ ታሪክ የምናውቀው ደጉ አብረሀም የተወለደው ያደገው ከጣኦት አምላኪ ቤተሰብ ነበር፡፡  እግዚያብሔርም አብርሀምን “አብርሀም አብርሀም ውጣ !እኔ ወደማሳህም ወደዚያ ተራራ ሂድ አለው”፡፡አብርሀምም ቤተሰቡ የሚያመልከው ጣኦት አይን እያለው የማያይ ጆሮ እያለው የማይሰማ “ልክ እንደ ኢህአዴግ”  ነበርና ከፈጣሪው የመጣለትን ትእዛዝ ሳያመነታ ተቀበለው ፡፡በሀጢያት ከረከሰው አካባቢውም ተለይቶ ወጣ፡፡አብርሀም ያደረገው ከሚወደው ቤተሰቡ  በባእድ አምልኮ አብሮ ላለመኖር የግድ መለየት ነበረበት ተለያም፡፡ዛሬ በተለያዮ የስልጣን እርከን በወታደራዊም ሆነ በሲቪል ተቋማት ከወያኔ ጋር እየሰራችሁ ያላችሁ ኢትዮጵያውያን ልክ እንደ አብረሀም በደም ከተበከለው ፤ህዝብን አፍኖ በችግር እየገደለ ካለው ስርኣት ራሳችሁ ለይታችሁ ውጡ፡፡አብርሀም ቅድስናን የተቀዳጀው ከባእድ አምልኮው ተለይቶ ነው፡ለጊዜያዊ ሥልጣን ጥቅም ወዘተ ራሳችህን እስካሁን አስገዛችሁ፡፡መጀመሪያ እውነት አለ መስሎአችሁ ገብታችሁ ይሆናል፡፡ግን ወያኔ ጋ ቀርቦ ያላየ የለም ደረጃው ይለያ እንጂ ፡፡ አንድም እውነት የለም ሁሉም ነገር የውሸት የማስመሰል ነው፡፡ወያኔ ጣኦት ነው፡፡ህገ-መንግስቱ፤የመለስ ራዕይ፤የብሄር መብት፤እድገት እና ትርናስፎርሜሽኑ፤የሚወራው ዲሞክራሲ ሁሉም ባእድ አምልኮዎች ጣኦቶች ናቸው፡፡እውነታውን ታውቁታላችሁ፡፡ስለገባችሁበት ነው እንጂ ሁሉም የህወአትን እድሜ ማራዘሚያ ነው፡፡ማንም ከወያኔ ጋር ሁኖ ህሌናው ያመነበትን እንደማይሰራ እናንተም ታውቁታላችሁ፡፡ፍርድቤቶች የሚፈርዱት በህሌናቸው ነው?ጋዜጠኞች እየሰራችሁ ያላችሁት እውነታውን ነው? ወታደሩ  የገንዛ ወንድሙን፣እህቱን  በቆመጥ የሚቀጠቅጠው አምኖበት ነው?፤የሚስኪኑዋ እናትክን ቤት እላይዋ ላይ የምታፈርሰው ህሌናህ ፈቅዶ በችግር ለተቆራመደው ወገናችን መርዳት ስንችል ለምን ተጨማሪ እዳ እንሆንባቸዋለን፡፡ከወያኔ ፍርፋሪ መጠበቅ ለጣኦት የተሰዋ መብላት ነው፡፡ ነው?ከወያኔ አገልጋይነት ተለዩ!ከወያኔ መንደር ውጡ!

‘ነውጥ አልባ ትግል’ – ጋዜጠኛ ኤልያስ ወንድሙ ስለ አዲሱ ጥናታዊ ፊልም ይናገራል – ሁሉም ሊያዩት የሚገባው

$
0
0

በአለም ዙርያ ተበታትነው ያሉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከነ ጋንዲ ምን ይማራሉ? የሳውዲ አረቢያ መንግስት በዜጎቻችን ላይ እያደረሱ ያሉት ግፍና መከራን እንዴት መቋቋም ይቻላል? በሌሎችስ ላይ እንዳይደርስ እንዴት መከላከል ይቻላል? – ‘ነውጥ አልባ ትግል’ ለእነዚህና ሌሎች ተዛማች ጥያቄዎች ምላሽ አለው – ጋዜጠኛ ኤልያስ ወንድሙ ስለዚሁ አዲስ ዶክመንታሪ ፊልም ይናገራል። አስተናጋጁ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ነው።

‘ነውጥ አልባ ትግል’ – ጋዜጠኛ ኤልያስ ወንድሙ ስለ አዲሱ ጥናታዊ ፊልም ይናገራል – ሁሉም ሊያዩት የሚገባው

የወያኔ ልዩ ፖሊስ በምስራቅ ሃረርጌ ዞን ንጹሃንን በጥይት ፈጀ

$
0
0

(ከምኒልክ ሳልሳዊ) በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልላዊ መንግስት ሚሊሻዎች የሆኑ እና “ልዩ ፖሊስ” በመባል የሚታወቁት የወያኔ የጸጥታ ሃይሎች በምስራቅ ሃረርጌ ዞን አራት ንጹሃን ዜጎችን ገለው ሁለት ማቁሰላቸው ታውቋል::እንዲሁም እስካሁን ቁጥራቸው ያልታወቁ ነዋሪዎች ከአከባቢው መፈናቀላቸው ታውቋል::

ባለፉት ወራቶች ጀምሮ የልዩ ፖሊስ ሃይሎች አከባቢውን በመውረር በዚሁ ምስራቅ ሃረርጌ በማዩ ሙሉጋ አከባቢ የሚኖሩ ንጹሃንን በማንገላታት በማሰር በመግደል የአከባቢውን ነዋሪዎች ከአከባቢው በማፈናቀል ላይ ሲሆኑ ይኸው ወረራ እና ማፈናቀል መግደል ጡምቢጎሃ ; ሴላጃጆ እና አናሚኖ;በስፋት እየተካሄደ ሲሆን አብዛኛው የአከባቢው ነዋሪዎች ቦታቸውን በመልቀቅ ይህንን የወያኔ ወረራ በመሸሽ ከአከባብያቸው ተፈናቅለው ወደ ቡርቃ ቲልጢላ እና የአከባቢ ወረዳዎች በመሸሽ ቦታቸውን የአከባቢው የወያኔ ሚሊሻዎች ወይንም ልዩ ፖሊስ ተቆጣጥሮት ይገኛል::

የሳምንቱ የአብርሃ ደስታ በፌስቡክ ላይ የተለቀቁ ምርጥ ጽህፎች

$
0
0

እኔ ምለው?!
——————

Abrha Desta‘የተምቤንና የዓጋመ ህዝቦች ባላቸው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ዓቅም የህወሓት ስጋት በመሆናቸው ይጨቆናሉ’ ብዬ በፃፍኩት ላይ ‘አብርሃ ትግራይ በአውራጃዊነት ለመከፋፈል ፈልጓል’ የሚል መልእክት ያላቸው አስተያየቶች ደረሱኝ።

እንዴት ነው ግን አከባቢን ጠቅሰን ችግር አለ ብንል ‘መከፋፈል’ ይሆናል? ወይስ በሁሉም አከባቢዎች ተመሳሳይ ችግር አለ? በመቀሌ የእሳት ቃጠሎ ችግር ካለ በዓዲግራት የሱኳር አቅርቦት እጥረት ሊኖር ይችላል። በየ አከባቢው ያለ ችግር ለየግል ቢነሳ መከፋፈል ነው?

ስለ ተምቤንና ዓጋመ በደል ስፅፍ ለምን ይህን ሁሉ ካድሬ ለየት ባለ መልኩ ተንጫጫሳ? የመከፋፈል ችግሩ ከሌለ እኔ በፌስቡክ ስለፃፍኩት ብቻ ትግራይ ልትከፋፈል ትችላለች? ስጋቱና መጨናነቁ ከየት መጣ? ይሄ ሁሉ የሚንጫጫ የፃፍኩት ነገር እውነት በመሆኑ አይመስላችሁም?

ትግራይ ትንሽ ነች። እንኳን ትግራይ (ትንሽ) ታላቋ ኢትዮጵያም እንድትከፋፈል አልፈልግም። እንዳውም የኔ ጥረት የህወሓትን የመከፋፈል ስትራተጂ መቃወም ነው። እኔ ትግራይን በአውራጃዊነት የመከፋፈል ፍላጎቱም ዓቅሙም የለኝም። በኔ የምትከፋፈል ትግራይም የለችም፤ ምክንያቱም ትግራይ ከ1968 ዓም ጀምሮ በህወሓት ተከፋፍላለች። የተከፋፈለች ትግራይ እንዴት እከፋፍላታሁ?

አሁንኮ ሽሬ አውራጃ የለም። በህወሓት ተከፋፍሏል። ዓጋመ አውራጃ የለም፤ ተከፋፍላል። እንደርታ አውራጃ የለም፤ ተከፋፍሏል። እንደርታ አሁን አውራጃ ሳይሆን አንድ ወረዳ ብቻ ነው። ተምቤን አውራጃ የለም፤ ተከፋፍሏል። የአሁኑ ተምቤንም ለሁለት ተከፍሏል፤ ደጉዓ ተምቤን ወደ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሲወሰድ ቆላ ተምቤን ግን በማእከላይ ዞን ስር ነው። ስለዚህ ተምቤን በሁለት የተለያዩ ዞኖች ነው የሚተዳደረው። ይህ በቅርቡ የተሰራ ተምቤኖችን የማዳከም ስትራተጂ ነው።

ስለዚህ ሁሉም የትግራይ አውራጃዎች በተበታተኑበት ወቅት እኔ የትኛው አውራጃ ነው የምከፋፍለው? ሁሉምኮ ተከፋፍሎ አልቋል። ያልተከፋፈለ ህዝብና አውራጃ እስቲ ንገሩኝ? ስለዚህ እኔ የምከፋፍላት ትግራይ የለችም፤ በህወሓት ተከፋፍላ አልቃለችና።

‘በሁሉም የትግራይ ክልሎች ጭቆና እያለ ለምን ተምቤንና ዓጋመ መረጥክ?’ ለሚለው ግን አስተያየት መስጠት ተገቢ ነው። አዎ! በሁሉም ቦታዎች ጭቆና አለ። የጭቆናው መጠንና ዓላማ ግን ይለያያል። በዓፋሮች ላይ የሚፈፀም ጭቆናና በአማራዎች የሚደርስ በደል ዓላማው አንድ ላይሆን ይችላል። ህወሓት የሽሬ ህዝብ፣ የሐውዜን፣ የእንደርታ፣ የራያ፣ የሑመራ፣ የኢሮብ፣ የአፅቢ፣ የዓድዋ፣ የአክሱም፣ የወልቃይት ወዘተ ህዝቦች ሲጨቁን ለመግዛት አልሞ ነው። የተምቤንና የዓጋመ ህዝቦች ሲበድል ግን ከመግዛት አልፎ ለስልጣኑ ስለሚያሰጉት ነው።

ሁሉም የትግራይ ህዝቦች በህወሓት የየራሳቸው የተለያየ ስም ወጥቶላቸዋል። በወጣላቸው ስምና ባህሪይ መሰረት አስተዳዳሪዎች ይላክላቸዋል። በተለያዩ አከባቢዎች የሚደርስ የተለያየ በደል ማንሳት ህዝቦችን መከፋፈል አይደለም።

ህዝቦች ሳነሳ ‘በአውራጃዊነት መከፋፈል ነው’ ካላች ሁኝ ግለሰቦችን ላንሳና ‘አብርሃ ትግራይን በግለሰቦች ደረጃ ለመከፋፈል እያሴረ ነው’ ብላች ሁ አስተያየት ለመስጠት እንዲመቻቹ።

በእንዳ አብርሃ ወ አፅብሃ አከባቢ የሚንቀሳቀስ ‘ዳደ’ የተባለ ሽፍታ ነበር። ህወሓቶች በጣም ይፈሩታል። ከደርግ ወታደሮች ጋር ለመፋለም ያልፈሩት የህወሓት ታጋዮች አንድ ግለሰብ ‘ዳደ’ ግን መድፈር አልቻሉም። እናም በስንት መከራ ህወሓቶች ትግራይን ከተቆጠጠሩ በኋላ ብዙ ወታደር ልከው ያዙት፤ ከዛ ግፍ በተሞላበት ተግባር አረዱት።

ህወሓቶች አንድ ግለሰብ ያስፈራቸው እንደነበር የምፅፈው አስፈላጊ ስለሆነ ሳይሆን ልክ የተምቤኖችና የዓጋሜዎች ያነሳሁት ያህል ‘በግለሰብ ደረጃ አትከፋፍለን’ የሚል አስተያየት ለመስጠት እንዲመች ነው። ታሪኩ ግን እውነት ነው።

ተምቤንና ዓጋመ
——————–

ስለ ተምቤንና ዓጋመ ህዝቦች አንስቼ ነበረ። ‘ግልፅ አይደለም’ የሚል አስተያየት ተሰጥቷል። አሁን ጉዳዩ ግልፅ ለማድረግ ግዜው አይደለም። ለመረጃ የሚሆን ግን እነሆ።

ከህወሓት የትጥቅ ትግል ወቅት ጀምሮ በትግራይ ክልል ከሚገኙ ህዝቦች ዓቅሙ እያላቸው በህወሓት የተንኮል አገዛዝ ምክንያት ተጨቁነው (ታፍነው) የሚኖሩ ህዝቦች የተምቤንና የዓጋመ ናቸው። የተምቤን ህዝብ የፖለቲካ ዓቅም አለው። የዓጋመ ህዝብም የኢኮኖሚ ዓቅም አለው። ሁለቱም ህዝቦች (የተምቤንና ዓጋመ) መቀስቀስ ከተቻለና አብረው ከሰሩ መላው ትግራይ አንቀሳቅሰው ህወሓትን ሙሉ በሙሉ ማሸነፍ ይችላሉ። ህወሓት አሁንም የሁለቱም ህዝቦች መነሳት ያስፈራዋል። ተምቤኖች በፖለቲካ እንዳይሳተፉ ይደረጋል፤ ዓጋሜዎቹም በኢኮኖሚ እንዲዳከሙ ይደረጋል። ተምቤኖች እንቅስቃሴ ጀምረዋል። ለዚህም ነው የህወሓት አስተዳዳሪዎች በተምቤን ለሚደረግ የስብሰባ ቅስቀሳ ለመረበሽ የተነሱት (የተምቤን አስተዳዳሪዎች የተምቤን ተወላጆች አይደሉም)። ህወሓት በተምቤንና ዓጋመ ምንም ድጋፍ የለውም። በጠመንጃ ሃይል ነው የሚገዛው።

‘ለውጥ የለም’?!
—————–

“አሁን ባለንበት ሁኔታ ‘ለውጥ የለም’ ብለን መከራከር እንችላለን?” አለኝ። በኢህአዴግ ዘመን የተገነቡ ህንፃዎችና አስፋልት መንገዶች ዋቢ በማድረግ ለውጥ መኖሩ የማይካድ እንደሆነ ሊነግረኝ ፈልጎ ነው።

ግን “ለውጥ የለም” ብዬ ማለት እችላለሁ። “ለውጥ የለም” ማለት ምን ማለት ነው? “ለውጥ የለም” ማለት ምንም የተሰራ ነገር የለም ማለት አይደለም። ለውጥ የለም ማለት ትምህርትቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ አስፋልት መንገዶች ወዘተ አልተገነቡም ማለት አይደለም። የመጣው ለውጥ ምን ያህል ነው? ባሁኑ ግዜ መታየት ያለበት ለውጥ ምን ያህል ነው? ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎች መመለስ አለብን እንጂ ለውጥማ ሁሌ ይኖራል። ለውጥ ላይኖር አይችልም። ሁሌ ለውጥ አለ። ለውጥ የተፈጥሮ ሕግ ነውና።

እንኳን ግብር የሚሰበስብ፣ ደሞዝ የሚከፈላቸው ሰራተኞች ያሉት መንግስት እያለ ማእከላዊ መንግስት ባይኖርም ህዝብ እስካለ ድረስ ለውጥ ይኖራል። ጉዳዩ መሆን ያለበት … ለውጡ ምን ያህል ነው? ከዚህ በላይ ለውጥስ ማምጣት ይቻላል ወይ? በኢኮኖሚው ዘርፍ ለውጥ ካለ በፖለቲካውስ ለውጥ አያስፈልግም ወይ? ወዘተ ነው።

‘ለውጥ የለም ወይ?’ የሚል ጥያቄ ሲቀርብልኝ የማስታውሳት ነጥብ አለች። (ደግሜ ልፃፋት)። ባልና ሚስት ነበሩ። የቤት ሰራተኛ ቀጠሩ። የቤት ሰራተኛዋ በሆነ ብር ወርሃዊ ደሞዝ ለባልና ሚስት ምግብ (ቁርስ፣ ምሳና እራት) እንድታዘጋጅ ተስማማች። ቤት ገባች። የመጀመርያው ቀን ቁርስ አዘጋጀች (ምሳና እራት አልሰራችም)። ባልና ሚስት ሆቴል ተጠቀሙ።

በሁለተኛው ቀን ምሳ አዘጋጀች (ቁርስና እራት የለም)። በሦስተኛው ቀን እራት አዘጋጀች (ቁርስና ምሳ የለም)። በአራተኛው ቀን ባልና ሚስት የቤት ሰራተኛዋን ጠርተው ምግብ እያዘጋጀች እንዳልሆነች ይነግሯታል። የቤት ሰራተኛዋም “እንዴት አልሰራም? ምግብ እየሰራሁ ነው” ብላ ትከራከራለች። ባል “ለምሳሌ ቁርስ ከሰራሽ ምሳ አትሰሪም፣ ምሳ ከሰራሽ እራት አትሰሪም” ይላታል። ሰራተኛዋ መልሳ “ሁሉም ሰርቻለሁ፤ የመጀመርያው ቀን ቁርስ አልሰራሁም? በሁለተኛው ቀን ምሳ አልሰራሁም? በሦስተኛው ቀን እራት አልሰራሁም? ሁሉም (ቁርስ፣ ምሳና እራት) ሰርቻለሁ” አለች።

ለሰራተኛዋ ምን መልስ አላቹ? ‘ቁርስ ወይ ምሳ ወይ እራት አልሰራሽም?’ አይባልም። ልንላት የምንችለው ‘ምግብ ማዘጋጀት ማለት በቀን ሦስቱም (ቁርስ፣ ምሳና እራት) ማዘጋጀት መቻል ነው’። ልንላት የምንችለው ‘ቁርስ አልሰራሽም’ ሳይሆን ‘በቀን መስራት የሚጠበቅብሽ ነገር አልሰራሽም። ስለዚህ የተቀጠርሺበት ምግብ የማዘጋጀት ስራ በአግባቡ እየተወጣሽ አይደለሽም። (ስለዚህ) አንድም ስራህሽን በአግባቡ ስሪ አልያም ደግሞ ዉጪና በቀን ቁርስ፣ ምሳና እራት ማዘጋጀት የምትችል ሌላ የቤት ሰራተኛ እንቁጠር’ ነው። (ሰራተኛዋ ኢህአዴግ ናት፤ ባልና ሚስት ደግሞ ህዝብ ናቸው)።

ኢህአዴግ ‘ለውጥ አምጥቻለሁ’ ሲለን ልክ እንደቤት ሰራተኛዋ ነው። ኢህአዴግ ለውጥ አላመጣም ስንል ምንም ዓይነት ለውጥ የለም ማለታችን አይደለም። እንደ መንግስት መስራት የሚገባውን እየሰራ አይደለም። ስለዚህ ሌላ ከኢህአዴግ በተሻለ መጠንና ፍጥነት መስራት የሚችል መንግስት ያስፈልገናል ነው ሐሳቡ።

ለውጥ ማእከላዊ መንግስት በሌለባት ሀገረ ሶማሊያም አለ። በሶማሊያ ለውጥ እየመጣ ስለሆነ መንግስት አያስፈልግም ወይም ሌላ ተጨማሪ ለውጥ አያስፈልግም ማለት ግን አንችልም። ሶማሊያ በኢንተርኔትና ቴሌፎን አገልግሎት አሰጣጥ ከኢትዮጵያ ትሻላለች። ኬንያና ሱዳን በመብራት ሃይል አገልግሎት ከኢትዮጵያ በደንብ ይሻላሉ። የኬንያና የሱዳን የገጠር ዜጎች ከኢትዮጵያውን በተሻለ ሁኔታ የመብራት አገልግሎት ያገኛሉ። ‘ኢትዮጵያ ለሱዳንና ኬንያ የኤለክትሪክ ሃይል ትሸጣለች’ ሲባል ገርሞኛል።

ኢህአዴግ የሰራው ነገር Physical Infrastructure ላይ ነው። ለምሳሌ የመንገዶች ግንባታ። የመንገድ ግንባታ የለውጥ መሰረት እንጂ በራሱ ለውጥ አይደለም። ምክንያቱም የአስፋልት መንገድ ግንባታው የለውጥ ዉጤት አይደለም። መንገዱ የተገነባው በሀገሪቱ በመጣ ዕድገት በተገኘ ካፒታል ሳይሆን በብድርና ባላስፈላጊ የገንዘብ ህትመት ምክንያት ነው።

የኢትዮጵያ አስፋልት መንገዶችና የባቡር ሃዲዱ ከየት በመጣ ገንዘብ ነው የሚገነባው? በብድርና በእርዳታ በተገኘ ገንዘብ ነው። ተበድረህ ገንዘብ አገኘህ ማለት ዕድገት አገኘህ ወይ ለውጥ አመጣህ ማለት አይደለም። (ግን ባግባቡ ተጠቅመህ በተበደርከው ገንዘብ ለውጥ ልታመጣ ትችላለህ፤ ሙስና ከሌለ ማለት ነው)። ኢህአዴግ የብድር ገንዘቡ ሲያቋርጠው ገንዘብ ያትማል። ገንዘብ ማተም ማደግ ወይ ለውጥ ማምጣት አይደለም።

በፖለቲካ ለውጥ የለም ሲባል ለውጡ በቂ አይደለም፣ የተሻለ ለውጥ ማምጣት ያስፈልጋል፣ ለውጥ እንፈልጋለን፣ ባለው ለውጥ አልረካንም ወዘተ ማለት እንጂ ምንም የተሰራ ነገር የለም ማለት አይደለም፤ ምንም ላይሰራ አይችልምና። ለውጥ ማስቆም እስካልተቻለ ድረስ ለውጥ ይኖራል።

በኢህአዴግ ዘመን ለውጥ አለ እንበል (እንተባበራቸው)። ለውጥ አለ እየተባለ ያለው ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ነው። ‘እኛ የምንፈልገው የኢኮኖሚ ለውጥ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ (የስርዓት) ለውጥም ያስፈልገናል’ ብንልስ? የኢኮኖሚ ለውጥ አስፈላጊ ነገር እንጂ የፖለቲካ ለውጥ የሚተካ በቂ መልስ አይደለም። የኢኮኖሚ ለውጥ ሲኖር የፖለቲካ ለውጥም ያስፈልጋል።

አንድ መንግስት በስልጣን ለመቆየት የሚያስፈልገው ነገር የኢኮኖሚ ለውጥ ማምጣት አንዱ ቢሆንም የፖለቲካ ተ አማኒነትም ያስፈልገዋል። ኢህአዴግ ‘መንገድና ባቡር ሃዲድ ስለገነባሁ በስልጣን መቀየት አለብኝ’ ብሎ ማለት የለበትም። የሀገረ አሜሪካ ዴሞክራቶችና ሪፐብሊካኖች በየአምስትና አስር ዓመት የሚቀያየሩ አንዱ ፓርቲ መንገድና ባቡር ሃዲድ መገንባት ስላልቻለ አይደለም። ከኢኮኖሚው ለውጥ በተጨማሪ የፖለቲካ ለውጥም ስለሚያስፈልግ ነው።

አሁን ካለው ለውጥ (ለውጥ አለ ብላቹ ለምትከራከሩ) የተሻለ ለውጥ ያስፈልገናል።

የአላሙዲን ሸራተን ሰራተኞች “መብታችን ተጣሰ” በማለት ሰላማዊ ሰልፍ ሊወጡ ነው

$
0
0

Sheraton Addis
(አዲስ አድማስ) የሸራተን አዲስ ሆቴል ሰራተኞች፤ የውጭ አገር ዜጋ በሆኑት የሆቴሉ ስራ አስኪያጅ የሚደርስብን ችግር ከአቅም በላይ በመሆኑ ሰላማዊ ሰልፍ ልንወጣ ነው አሉ፡፡ ከዚህ በፊት የመብት ጥሰት እንደደረሰብን ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ለሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በደብዳቤ ብንገልፅም ምላሽ ባለማግኘታችን በድጋሚ ደብዳቤውን አስገብተናል ብለዋል – ሰራተኞቹ፡፡
በትምህርት ደረጃና በእውቀት ከሀበሾቹ የማይበልጡ የውጭ ዜጐች አሰሪዎቻችን ያንቋሽሹናል፤ ዛሬ ፆም ነው ይህን አንበላም ስንል “ድሮ ረሀብተኞች ስለነበራችሁ ረሀባችሁን ለማስታወስ የምታደርጉት ነው” ይሉናል፤ ጥቅማጥቅሞቻችን አይከበሩም፣ እድገት እንከላከላለን ያሉት ሠራተኞቹ፤ “ፈረንሳዊው ስራ አስኪያጅ ዲፓርትመንቶችን በመበታተን፣ ሰራተኞችን ወዳልፈለጉትና ወደማይመለከታቸው ቦታ ይመድባሉ፤ ይህን ስንቃወም እስከመደብደብ እንደርሳለን” ብለዋል፡፡
“የዜጐች ደህንነት ጥበቃ ከአገር ውስጥ ይጀምራል፤ በአገራችን ነጮች እያንቋሸሹን እና ሞራላችን እየተነካ ነው” የሚሉት ሰራተኞቹ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ችግራችንን በዝምታ ማለፋቸው አሳዝኖናል ብለዋል፡፡
“ችግራችን ሲብስ ፒቲሽን ተፈራርመን ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያስገባነው ደብዳቤ፤ ለሆቴሉ ስራ አስኪያጅ ለሚስተር ዦን ፒይር ማኒንጐፍ ከደረሰ በኋላ፣ ስቃያችን በዝቷል ያሉት ሰራተኞቹ፤ አንድ ነገር ለማስፈቀድ፣ አቤቱታ ለማሰማትና ለእድገት ለመወዳደር ስንጠይቅ ስራ አስኪያጁ ፒቲሽን የፈረሙትን ሰራተኞች ስም ያወጡና “በእኔ ላይ ፈርመሀል፤ እድሜ ልክህን እድገት አታገኝም፣ ይህ አይፈቀድም” እያሉ እንደሚያንገላቷቸው ተናግረዋል፡፡ ሸራተን አዲስ ሆቴል ከ800 በላይ ቋሚ ሰራተኞች እንዳሉት የገለፁት ሰራተኞቹ፤ ይህ ሁሉ ሰራተኛ ባለበት ስራ አስኪያጁን ጨምሮ አንዳንድ የውጭ አሰሪዎቻችን እያንጓጠጡንና ጫና እየፈጠሩብን ስለሆነና የሚመለከተው የመንግስት አካል ምላሽ ስላልሰጠን በቅርቡ ሰላማዊ ሰልፍ ለመውጣት አስበናል ብለዋል፡፡
የሆቴሉ ሰራተኞች ማህበር ሊቀመንበሩ አቶ ዳንኤል አለሙ ታሪኩ በበኩላቸው፤ “ሰራተኞቹ ከማህበሩ ወጥተው በራሳቸው ተደራጅተዋል፤ ነገር ግን ማኔጅመንቱና ሰራተኛው ተቀራርበው እንዲሰሩና በውይይት ችግራቸውን እንዲፈቱ ብዙ ርቀት ብንሄድም የሆቴሉ ስራ አስኪያጅ ሚስተር ዦን ፒይር ማኒንጐፍ ፈቃደኛ አልሆኑም” ብለዋል፡፡
የሆቴሉን ስራ አስኪያጅ ሚስተር ዦን ፒይር ማኒንጐፍን ለማነጋገር ብንሞክርም እረፍት ላይ በመሆናቸው ሳይሳካልን ቀርቷል፡፡ ሌላ ሃላፊ ለማነጋገር ፀሃፊዋን ጠይቀን፤ በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሚሰጡት ስራ አስኪያጁ ብቻ እንደሆኑ ገልፃልናለች፡፡

ምንጭ ዛሬ በአዲስ አበባ የታተመው አዲስ አድማስ ጋዜጣ

በሳዑዲ አረቢያ 80ሺህ ኢትዮጵያውያን እጃቸውን በሰላም እንዲሰጡ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጠየቀ፤ ሳዑዲዎች አዲስ ዘመቻ ጀምረዋል (አዳዲስ መረጃዎች)

$
0
0

(ዜና ትንታኔ ኢትዮጵያ ሃገሬ ከጅዳ በዋዲ)

በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ አምባሳደር ዘነበ ከበደ የሚመሩት የመንግስት ሹማምንቶች ጅዳ ከተማ ውስጥ፡ መሽገዋል ያሏቸው 80 ሺህ ኢትዮጵያውያን እጃቸውን በሰላም ካልሰጡ የመንፉሃው አይነት እልቂት እንደሚጠብቃቸው ሲያሟርቱ! ሪያድ በኢትዮጵያው አምባሳደር መሃመድ ሃሰን የሚመራው ቡድን የሚያሰማው « ጅብ ከሄድ ውሻ ጮህ ጥሪ » ድብቅ አጀንዳ ያለው መሆኑ ተገለጸ::

ከ9 ሚልዮን በላይ የተለያዩ የውጭ፡ሃገር ዜጎች በጥገኝነት እንደሚኖሩባት የምትታወቀው ሳውዲ አረቢያ በህገወጥ መንገድ የሚኖሩ የውጭ ሃገር ዜጎች የመኖሪያ ፈቃዶቻቸውን እንዲያስተካከሉ የተሰጠ የ 7 ወር የግዜ ገደብ መጠናቀቅን ተከትሎ የሳውዲ ጸጥታ ሃይሎች ኢትዮጵያውያኑ ላይ ብቻ ባነጣጠረ እርምጃ እስካሁን ቁጥሩ በወል ለማይታወቅ ወገናችን አሰቃቂ ህልፈተ ህይወት ስቃይ እና መከራ ምክንያት መሆኑ ይታወቃል። በተለይ ሪያድ ከተማ በተለምዶ መንፉሃ እየተባለ የሚጠራ ሰፈር ሃገራቸው ለመግባት ጥያቄ ባቀረቡ ወገኖቻችን እና በሳውዲ ጸጥታ ሃይሎች መሃከል በተነሳ ግጭት አያሌ እህቶቻችን በአረብ ጎረምሷች ተደፍረዋል እህቶቻቸውን እና ሚስቶቻቸውን ለመከላከል ጩሀታቸውን ያሰሙ ንጽሃን ወገኖች በአሰቃቂ ሁኔታ በሳንጃ እና በጓራዴ ተገድለዋል ፡፤
neb 7
ይህንንም ተከትሎ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻች ከአሰቃቂው ጥቃት እርሳቸውን ለመታደግ ከዳር እስከዳር «ሆ »ብለው አደባባይ በመውጣት የሳውዲ አረቢያ አውራጎዳናዎችን በማጨናነቅ የአለምን መገናኛ ብዙን ሽፋን በማጝት በሳውዲ አረቢያ በጠራራ ፀሃይ እና በሌሊት በወገኖቻችን ላይ ሲፈጸም የነበረው ጭፍጨፋ ስቃይ እና በደል በሃገር ውስጥ እና በውጭ ሃገር የሚገኙ ወገኖቻቸውን ዘንድ ቁጣን በመቀስቀስ በሳውዲ መንግስት ላይ ባደረጉት ተጸዕኖ በማን አለብኝነት በወገኖቻችን ላይ ሲፈጸም የነረውን ኢሰባዊ ድርጊት ለግዜውም ቢሆን ጋብ እንዲል አስችሏል።

የኢትዮጵያኑ አለማቀፍ ቁጣ ያስደነገጠው የሳውዲ አረቢያን መንግስት በሚልዮን ለሚቆጠሩ የውጭ፡ሃገር ያወጣው ህግ በኢትዮጵያውያኑ ላይ ብቻ እንዲያትኩር አስገድዶታል። ይህ በዚህ እንዳለ እስካሁን በመቶሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያ ውያን ስደተኞች የስውዲ አረቢያን ምድር በሰላም ለቀው ለሃገራቸው እንደብቁ የሚናገሩ ምንጮች አሁንም 80 ሺህ ህገወጥ ኢትዮጵያውያን ጅዳ ጣይፈ መካ መዲና ከተሞች ውስጥ መሸገዋል ተብሎ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት እይተሰጠ ያለው መግለጫ ቅንነት የጎደለው መሆኑንን ይገልጻሉ። በሃጂ እና ኡምራ አሊያም በባህር ወደ ሳውዲ ምድር ድንበር አቅርጠው ገብተውል ተብለው የሚነገርላቸው ኢትዮጵያውያን ያሉበትን ሁኔታ የማይዘረዘረው በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንላ የመንግስት ሹማምቶች መግለጫ ህገወጥ የተባሉት ወገኖች በግዜ እጃቸውን ሰጠተው ወደ ሃገር ካልተመልሱ በሪያድ መንፉሃ የተከሰተው አይነት አልቂት እንደሚገጥማቸው አስጠንቅቀዋል።

ይህ በቆንስል ዘነበ ከበደ የሚመራው ጽ/ቤት ሰሞኑንን እያሰማን ያለው ጩህት ወገናዊነት የጎደለው እና ሳውዲያኖቹ በኢትዮጵያውያኑ ላይ ብቻ በማነጣጠር መኖሪያ ፈቃድ ያላቸውን ኢትዮጵያውያን ጭምር ከሳውዲ ምድር ጠራርጎ ለማስወጣት የተያዘ እቅድ አንዱ አካል መሆኑንን የሚናገሩ የጅዳ ነዋሪዎች የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸው ወገኖች በሳውዲ ምድር በሰላም ሰርቶ የመኖር ህልውናቸው አስተማማኝ ባልሆነበት አጋጣሚ እንደዚህ አይነት መግለጫ ማውጣት ሃላፊነት የጎደለው መሆኑንን ይናገራሉ። እንዚህ ወገኖች የጅዳው ቆንስላ ጽ/ቤት እንደዚህ አይነት አስገራሚ መረጃ በአረብኛ እና በአማርኛ ቋንቋ በተዘጋጁ በራሪ ወረቅቶች ቅስቀሳ ማካሄዱ ትላንት ሪያድ ከተማ መንፉሃ ውስጥ፡ቆጨራ እና ሳንጃ ታጥቀዋል የሚል የተሳስተ መለዕክት በማስተላለፍ ወገኖቻቸውን ካስፈጁት በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያው አንባሳደር መሃመድ ሃሰን ከፈጸሙት ስህተት የማይለይ መሆኑንን ይገልጻሉ።
saudi arabia today
በሌላ በኩል ሰሞኑንን በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ በየጥጋጥጉ ማስታወቂያዎችን በመለጠፍ እና በራሪ ወረቀቶች በመበትን እያሰማ ያለው የተለመደ የአዞ እንባ « ጅብ ከሄደ ውሻ ጮህ » መሆኑንን የሚገልጹ የአካባቢው ነዋሪዎች የምህረቱን አዋጅ ተከትሎ ጉዳዮቻቸውን እስካሁን ማስፈጸም ተስኗቸው በሳውዲ አረቢያ ውስጥ ለመኖር የሚያስችሏቸውን ማመዘኛ ያላሞሉ ወገኖች በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ እየቀረቡ ምዝገባ እንዲያካሂዱ የሚለው መለዕክት ለኢትዮጵያውያኑ ታስቦ ሳይሆን ዲፕሎማቱ የተለመደውን ድብቅ አጀንዳቸውን በቀሪው ኢትዮጵያዊ ወገናችን ላይ ለማስፈጸም እንደሆነ ይናገራሉ።

በተለያዩ አቅጣጫዎች ያለደረስኝ፡በወገኖቻችን ሽፋን በመቶሺ የሚቆጠሩ ሪያሎችን በመሰብሰብ ላይ የሚገኘው በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ዲፕሎማቶች ከተጠቀሱት ወገኖች ኪስ ለተለያዩ ገዳዮች ማስፈጸሚ የሚውል ገንዘብ ለመሰብሰብ እቀድ እንዳላቸው ውስጥ አዋቂ ምንጮች ይገልጻሉ። ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም በወገኖቻችን ላይ ለተፈጸመው አስቃቂ ግድያ ግፍ እና በደል ተመጣጣኝ እርምጃ እንደሚወስድ የገቡትን ቃል ከፖለቲካ ግብአትነት እንደማያልፍ የሚናገሩ ወገኖች የኢትዮጵያ መንግስት በሳውዲ አረቢያ መንግስት ላይ ያሳረፈው ምንም አይነት ዲፕሎማሲያዊ ተጽእኖ ባለመኖሩ ሳዑዲያኑ ለኢትዮጵያውያኑ ያላቸው ጥላቻ አገርሽቶ በሪያድ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን «በእስፖንሰሮቻቸው» የመኖሪያ ፈቃዳቻቸው በመሰረዙ አያሌ ወገኖች ለህገወጥነት እየተዳረጉ መሆናቸው ይነገራል።

የቀድሞው ጠ/ሚ/ር ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ መጽሐፍ ጻፉ

$
0
0

ከክንፉ አሰፋ (ጋዜጠኛ)
fikresilase wegderese new book cover ፀሃይ አሳታሚ ድርጅት በታኅሣሥ 16, 2006 ዓ/ም (Dec. 25, 2013) የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩትን የሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስን ‘እኛና አብዮቱ’ የሚል መጽሃፍ ለገበያ እንደሚያበቃ አስታወቀ። ሻምበል ፍቅረሥላሴ እንደ ደርግ አባልነታቸው በጋራ ያመኑበትን፣ የተማከሩትን፣ የወሰኑትን፣ የሰሩትን፣ የገጠማቸውንና በቅርብ በዓይን ምስክርነት ያዩትን ተንትነው በ‘እኛና አብዮቱ’ ያስነብቡናል። የራሳቸውን ዕይታ ያካፍሉናል።

ልጅ ሆነን አንድ አባባል እሰማ ነበር።”አበላል እንደ ደርግ አባል። አለባበስ እንደ ፍቅረሥላሴ ወግደረስ!” – የሚል። በተለይ በኔ ትውልድ ያለን ሰዎች፣ ከዚህ ውጭ ስለኝህ ሰው የምናውቀው ብዙም ነገር አልነበረም። ግና እኝህ ሰው በልባቸው መክሊት ለአመታት የቋጠሩትን መረጃ ጀባ ሲሉን፤”… አጻጻፍም እንደ ፍቅረሥላሴ ወግደረስ” የሚያሰኝ ሆኖ አገኘሁት።

ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ለአስራ አምስት ዓመታት አብዮቱን ሲመሩ ቆይተው ወደ መጨረሻው ከሥልጣን በጡረታ ስም እንዲሰናበቱ ተደርገዋል። ደርግን በጣለው በወያኔ መንግሥትም ለ፳ ዓመታት ታስረው፣ የሞት ፍርድ የተበየነባቸውና በመጨረሻ ፍርዱ ወደ ዕድሜ ልክ ተዛውሮላቸው ከእሥር ቤት በአመክሮ የወጡ ግለሰብ ናቸው።

ጸሃፊው በድራማ መልክ በመጽሃፋቸው ካሰፈሩዋቸው እውነታዎችና ግለ-ሂሶች ውስጥ አንዳንዶቹን ለአንባቢያን ማካፈሉ አይከፋም። ደርጎች መፈንቅለ መንግስት አድርገው ሲያበቁ ቀዳማዊ ሃይለስላሴ ዘንድ ቀርበው ከንጉሱ የገጠማቸውን አስገራሚ ምላሽ ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ በመጽሃፋቸው እንዲህ ሲሉ አስፍረዋል።

የፖለቲካ እሥረኞች በሙሉ እንዲፊቱ የሚለው ጥያቄ እንደተነበበ ንጉሡ ጣልቃ ገብተው “ለመሆኑ የፖለቲካ እሥረኞቹ እነማን ናቸው?” የሚል ጥያቄ አቀረቡ። “በእርግጥ የምናውቃቸው የፖለቲካ እሥረኞች ባይኖሩም ማንኛውም የፖለቲካ እሥረኛ እንዲፈታ ነው የምንጠይቀው” አሉ ሻለቃ ተስፋዬ ገብረኪዳን። ንጉሡ ራሳቸውን ነቅነቅ አድርገው ጽሑፉን የሚያነበውን የደርግ አባል እየተመለከቱ “አልገባችሁም!” ብለው ዝም አሉ። በእርግጥም አልገባንም። ተማሪዎችና የተለየ ዓላማ የነበራቸው የተማሩ ሰዎች የሰነዘሩትን መፈክር ብቻ ነበር ይዘን ንጉሡ ፊት የቀረብነው። በፖለቲካ እሥረኝነት ስም በከፍተኛ ደረጃ ለጣሊያን ወራሪ መንግሥት በባንዳነት አድረው አገራችንን የወጉ፣ ለቅኝ ተገዥነትም የዳረጉትን እንደ ኃይለሥላሴ ጉግሳ ያሉ ወንጀለኞች የፖለቲካ እሥረኞች ተብለው ከግዞትና ከእሥር ቤት አስወጥተን እንደ ጀግና ራሳቸውን እንዲቆጥሩ አደረግናቸው።

የነ ጄነራል ተፈሪ በንቲ ጉዳይን አስመልክቶ የሰፈረው ታሪክ ደግሞ እንዲህ ይነበባል።

“በሊቀመንበርነት ስብሰባውን የሚመሩት ጄነራል ተፈሪ ‘የቋሚ ኮሚቴው’በዛሬው ቀን የሚወያይበትን ጉዳይ አስመልክቶ የመቶ አለቃ ዓለማየሁ የደርጉ ዋና ፀሐፊ ይገልጽልናል’ ብለው ስብሰባው መጀመሩን ካበሰሩ በኋላ ዓለማየሁ በአጀንዳው ላይ አጭር ገለጣ ማድረግ ሲጀምር ስልክ ተደወለ። ስልኩ ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ አጠገብ ስለነበር ወዲያው ቅጭል እንዳለ መነጋገሪያውን በማንሳት ሃሎ አሉ። ከሌላው ጫፍ ማን እንደደወለ አላወቀንም። በኋላ እንደታወቀው ሌ/ኮሎኔል ዳንኤል ነበር የደወለው። ምን እንደተነጋገሩ አልተሰማም። ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ብቻ “እሺ እሺ” ብለው ስልኩን ዘጉት። ስልኩን እንደዘጉ “ይቅርታ ስልኩ የተደወለው ከጎንደር ነው። ጎንደር ውስጥ ችግር አለ። እናንተ ቀጥሉ” ብለው ከጀርባቸው ባለው በር በኩል ውልቅ አሉ። በዚህን ጊዜ ዓለማየሁና ሞገስ ጥርጣሬ የገባቸው መሰለ። ዓለማየሁ ንግግሩን አቋርጦ በመስኮት በኩል ውጭ ውጭዉን መመልከት ጀመረ። ዓይኖቹ አላርፍ አሉ። ግራና ቀኝ ይመለከታል። አጠገቡ ያሉትን ሰዎች ሁሉ በጥርጣሬ ተመለከተ። ሻምበል ሞገስም በር በሩን ይመለከታል። ከአሁን አሁን አንድ ችግር ይከሰታል የሚል ፍርሃት ያደረበት ይመስላል። ሁሉም የኢሕአፓ አባላትና ደጋፊዎች ፈርተዋል። እንደፈሩት አልቀረም ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ከወጡ ሁለት ደቂቃ እንኳን አልሞላም ከበስተጀርባ ባለው ኮሪደር የወታደሮችን እርምጃ ሰማን። ወታደሮች ሲንቀሳቀሱ በፊት ለፊታችን ባሉት መስኮቶች በኩል ተመለከትን። በዚህን ጊዜ ፍስሐ ደስታ “ተከብበናል” አለ። ወዲያው ሁለቱም በሮች በኃይል ተበረገዱ። ሁላችንም ደነገጥን፣ ቀልባችን ተገፈፈ፣ እጢአችንም የወደቀ መሰለን። ድርቅ ብለን በተቀመጥንበት ቀረን።…

ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ሰለ ልጅ ሚካኤልን አስተዋይነት ሲያስታውሱ እንዲህ የሚል ግለሂስም ያስነብቡናል።
እኛ በችኮላ ውሳኔ መስጠታችን፣ ሕዝቡን በደንብ አለማወቃችን፣ ሰፊ የሕዝብ አመራር ልምድ ማጣታችን፣ የአገርና የውጭውን ፖለቲካ ውስብሰባዊ ግንኙነት አለመገንዘባችን፣ የመንግሥትን አሠራር ደንብና ሥርዓት አለመረዳታችን፣ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ጥመርታዊ ግንኙነትን መመልከት አለመቻላችን፣ የተለያየ ገንቢም ሆነ አፍራሽ ተልዕኮ ያላቸው ኃይሎች ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩብ ያለማጤናችን፣ በየዋህነትና በቅንነት ብቻ እንደምንሠራ በመገንዘባቸው ሊሆን ይችላል ልጅ ሚካኤል ከእኛ ጋር መቆየት የሚችሉት ለአጭር ጊዜ ብቻ እንደሚሆን የጠቆሙት…

በወቅቱ ስለ ህዝቡ የእርስ በርስ መጨካከንና መወነጃጀል ባሰፈሩት ክፍል ውስጥ እንዲህ የሚል ታሪክ እናገኛለን።

..የሥራ ዕድገት የተከለከለ፣ በሌብነትም ሆነ በስካር ወይም በሌላ ጥፋት የተቀጣ፣ በግል ጉዳይም ሆነ በመንግሥት ሥራ ከአለቃው ጋር የተጣላ፣ በአጋጣሚው ተጠቅሞ አዲስ ሹመት ወይንም ዕድገት ለማግኘት የሚፈልግ ሁሉ ጠቋሚ፣ ወንጃይ፣ ከሳሽ፣ ተበዳይ ነው።

የተወሰነ ጥቅም ለማግኘት ወይም ሌላውን ለመጉዳት ብለው “ኢትዮጵያ ትቅደምን ይቃወማል፣ ከታሠሩት ባለሥልጣናት ወይም ሚኒስትሮች የቅርብ ዝምድና አለው። ስለሆነም ሥራ ይበድላል፣ ሠራተኛውን ያጉላላል፣ ውሳኔ አይሰጥም” በማለት አለቆቻቸውን የሚከሱ፣ የሚወነጅሉ በርካታ ናቸው። ለደርግ አባላት ቤታቸው ድረስ በመሄድ በማስረጃ የተደገፈ ቢሆንም ባይሆንም ተቆርቋሪ በመምሰል የክስ ማመልከቻ የሚያቀርቡም ነበሩ። እንታሠራለን ብለው በፍርሃት የተደበቁ ባለሥልጣናትን የቅርብ ዘመዶቻቸው ወይም አሽከሮቻቸው ወይም ጎረቤቶቻቸው ደርግ ጽሕፈት ቤት ድረስ በመምጣት ያጋልጧቸው ነበር። የመሥሪያ ቤቶችን ሰነዶች ፎቶ ኮፒ በማድረግ ወይም ሰነዱን እንዳለ ከፋይሉ አውጥተው በማቅረብ “በመንግሥት ንብረት፣ ሀብት ወይንም ገንዘብ ላይ አላግባብ ተወስኗል” ብለው ጥቆማና መረጃ የሚያቀርቡም ነበሩ። ሠራተኞች አሠሪዎቻቸውን ይከሳሉ፣ ይወነጅላሉ። ገበሬዎች ለዘመናት በደል አደረሱብን የሚሏቸውን የአካባቢ ባለሥልጣናት ይወነጅላሉ። ውንጀላው በርካታ ነው።

አሽከሮች፣ ዘበኞች፣ ገረዶች… መረጃ ይሰጣሉ፣ ይጠቁማሉ። የተደበቀ የጦር መሣሪያ፣ የተደበቀ ገንዘብ፣ ወደሌላ ቦታ የተወሰደ ወይም የሸሸ ሀብት እንዳለም የሚጠቁሙን እነሱ ናቸው። በአንድ ቦታ በርከት ያሉ ሰዎች ተሰብስበው ምሽት ከአሳላፉ “ሲያድሙ ነበር” ብለው ከነስም ዝርዝራቸው መረጃውን ደርግ ጽሕፈት ቤት ድረስ ያመጣሉ። “እኛ እስከዛሬ የበይ ተመልካች ነበርን ዛሬ ዕድሜ ለእናንተ እንጀራ ሊወጣልን ነው! ከእናንተ ጎን ተሰልፈን አቆርቋዦቹን እንታገላለን! በማንኛውም ጊዜ ትዕዛዝ ብትሰጡን ለመፈጸም ዝግጁ ነን!” እያሉ ታማኝነታቸውንና ተባባሪነታቸውን የሚገልጡም ብዙዎች ነበሩ። በጣም የሚያስደንቀው አባቶቻቸውን፣ ልጆቻቸውን፣ ወንድሞቻቸውን፣ እህቶቻቸውን፣ ባሎቻቸውን፣ ሚስቶቻቸውን በመክሰስ፣ በመወንጀል፣ በማጋለጥ፣ በመጠቆም ብሎም በማሳሰር ጉዳት ያደረሱ በርካቶች መሆናቸው ነው።

እንግዲህ ስለ አዲሱ ‘እኛና አብዮቱ’ መጽሃፍ ይህንን ካልኩ ቀሪውን ለአንባቢ መተው ይበጃል። ሁሉም ሰው መጽሃፉን አንብቦ የራሱን ፍርድ ይስጥ።

ህይወት በሩጫ ትመሰላለች። የተፈጥሮ ህግጋት ነውና የሰው ልጅ እስትንፋሱ እስኪቋረጥ ይሮጣል። ከዚያም ሩጫውን ይጨርሳል። ሩጫውን ሳይጨርስ በልቡ ቋጥኝ የያዘውን እምቅ ቋጠሮ የሚተነፍስ ደግሞ እድለኛ ነው። በአንጻሩ ደግሞ በአእምሮው የቋጠረውን የእውቀት ምስጢር ሳያካፍል የሚያልፍ ሁሉ ያሳዝናል። ያለውን የወረወረ ንፉግ አይደለምና መንቀፍም ካለብን የሚወረውረውን ሳይሆን የማይወረውረውን ነው። መተቸት ካለብነም ሃሳቡን እንጂ ግለሰቡን ባይሆን ይመረጣል። በሃሳብ ላይ መወያየትና መተሻሸት ደግሞ አዋቂነት ነው።

በመጨረሻም የመጽሃፉ አርታኢ ኤልያስ ወንድሙ በመግቢያው ላይ ባሰፈረው መልእክት ጽሁፌን ልቋጭ።

የተማረ፣ ያወቀና ያደገ ትውልድና ዜጋ ምልክቱ የተጻፈን ማንበቡ፣ ያነበበውን ማብላላቱና ካነበበው ውስጥ ስንዴውን ከእንክርዳዱ መለየቱ ሲሆን፤ እራሱም አስተውሎና አገናዝቦ መጻፉ ደግሞ መማሩን ብቻ ሳይሆን መመራመሩንና ማወቁን የሚያሳይ ታላቅ ተግባር ነው። ለዚህም ደግሞ ግላዊ ነጻነት ያስፈልገዋልና ጫንቃው ላይ ያሉትን ግላዊና ታሪካዊ ቀንበሮች የሰበረ ነጻ ሰው መሆን ይጠበቅበታል። ትምህርትና ዕውቀት አስተዋይነትንና ጥልቀትን ከራስ በላይ ለትውልድ አሳቢነትን የሚያመለክት ታላቅ ኃላፊነት ነው። ለዚህም እንደ ትናንቱ ‘የተማረ ይግደለን’ ሳይሆን፤ የተማረ ያስተምረን፣ ያስተዳድረን ብሎም ይምራን በምንልበት ዘመን ከምናነብበው ውስጥ ያልተስማማንበትን በጨዋነት የመቃወም፣ የፈቀድነውን እንደ ስሜታችን የመደገፍና ተሳሳተ የምንለውን ለእርማት መጠቆም ግላዊ መብታችን ነው።…

* ፀሃይ አሳታሚ ድርጅት ከዚህ በፊት የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያምን፣ የቀድሞውን የህወሃት መሪ ዶ/ር አረጋዊ በርሄን፣ የቀድሞውን የኢህአፓን አመራር አባል የዶ/ር መላኩ ገኝን፣ የቀድሞው ሚንስትር የአቶ ተካልኝ ገዳሙን መጽሃፍትና ከስልሳ በላይ የሆኑ በኢትዮጵያ ታሪክና ጥናት ላይ ያተኮሩ መጽሃፍትን ማሳታሙ ይታወሳል። ‘እኛና አብዮቱ’ የሚለው ይህ አዲስ መጽሃፍ በwww.tsehaipublishers.com ድረገጽና በቀርቡ በየሱቁ አንደሚገኝ ከሎስ አንጀነሰ የደረሰን ዘገባ አስታውቋል። ሁላችንም ገዘተን እናንብብ።

መጽሃፉን አንብቤ እንደጨረስኩ በሂሳዊ ግምገማ እመለስበታለሁ።


የተሳካ ትርጉም ያለው –እንቅስቃሴ በሲቢሊቲ ሩም። ሥርጉተ ሥላሴ

$
0
0

ሥርጉተ ሥላሴ 22.12.2013

sreate1ዕለቱ ሰንበት የተቀደሰ የተወደደ በፈጣሪው የተመረጠ ነበር። በዲኔግዲ አማክኝነት ሸገር የዘገበው የታልቅ ሚስጢር ዕውነተኛ ቀን ነበር 08.12.2013። በዚህ ሰዓት ነበር አባ መላ /አቶ ብርኃኑ ዳምጤ/ የሩሙ ባላቤት እጅግ በተመሰጠና ተቆርቆሪነቱ በአዬለ ሁኔታ በዕለቱ ስልኩን ፈልጎ ቃላቸውን በጀሯችን ያደረሰን። ስደት ደስታን የሚገፍ ሲሆን ያን ቀን ግን እውነተኛ ደስታ ነበር የተሰማኝ ከደስታም በላይ ሐሴት። በወቅቱ „ኢትዮጵያዊነት የታላቁን የሰላም አባት የኔልሰን ማንዴላ ህይወት የታደገ ታላቅ ሚስጢር …. አነጠረ።“ በሚል አንድ መታጥፍ ቢጤ ጽፌ ዘኃበሻም ታድጎኝ ለንባብ በቅቶ ነበር አመስግናለሁም።

አባ መላ ጥሩ ተናጋሪ ነው። ንግግር ሥነ – ጥበብ ነው። ጸጋም ነው። ተሰጥዖ። ሥጦታውም የማዳህኒዓለም ቢሆንም በክህሎት፤ በስልጠና ሥነ ደንቦችን በማጥናት ማሳደግ የሚቻል ጉልበታም ፊኖሚና ነው። ንግግር አድማጭን ወደ ተፈለገው አቅጣጫ የሚመራ የተዋጣለት መሪ ነው። ጥሩ ንግግር … በእጅ ያለ ወርቅ ነው። ጥሩ ንግግር ገዢ መሬት ላይ አለ አጥቂ ሰራዊት ነው። ይህን ለመልካም ተግባር ካዋሉት ውስጥ ዕውቅ የዓለማችን ሰዎች ውስጥ ኪንግ ማርቲን ሉተር፤ ፕሬዚዳንት አብርኃም ሊንከን፤ ማህተመ ጋንዲን ትናት፤ ዛሬ ደግሞ ፓኪስታናዊዋ የ16 ዓመቷ ታዳጊ ወጣት የታለቢና ጥቃት ሰለባ ሆና ከሞት የተረፈቸው ማላለ ለምሳሌነት ብናነሳ … ለጥፋት ደግሞ ጀርማናዊ አዶልፍ ሂትለር – ለናኒዝም፤ ሞሶሎኒ – ለፋሺዝም ተግባራዊነት ህዝብን በምዕላት ያንቀሳቀሱበት ታላቅ መሳሪያ ነው።

እኔ የአባ መላን የንግግር ጸጋ የማዬው ከዚህ አንጻር ነው። አባ መላ የተዋጣለት ተናጋሪነቱ ብቻ ሳይሆን የድምጹ ቃና ሳቢነት፤ እንዲሁም ሳቁ እራሱ ውበት አለው። ጥሩ ተናጋሪ ልብን ገዝቶ፤ ግርቶ ወደ ተፈለገው አቅጣጫ የመምራት ሞገዱ ሆነ አቅሙ መጠነ ሰፊ ነው። የአባ መላ የመታገስ አቅም፤ ኦዲዬንስ እንደ ባህሪው ለማስተናገድ ያለው ስልት፤ ከተረብ ጋር ይመቻል። የነፃነት ጉዞም ምልክት ነው – ለእኔ። የተመቸንና ያልተመቸን ኃሳብ አንዱ ለሌላው ቢጎረብጠውም አለስልሶ እውነትን አሸናፊ የማደረግ ኃይሉ ዓምድ ነው። አንድ ጊዜ እንደ ዋዛ „ከአባይ በፊት ሽሮ ይገደብ“ ሲል አዳምጥኩት። ይህ ቅኔ ነው። ዛሬ ኢትዮጵያ ላይ ወፈር ያለ ሽሮ ሰርቶ ለመብላት እንኳን ያልተቻለበት የተፋቀ ዘመን ስለመሆኑ እዬሳቀ ግን መንፈስን ሰርስሮ የገባ ሥነ – ቃላዊ አገላላጽ ነበር። ይህ አገላለጽ ህሊናን በአግባቡ የማዘጋጀት ስበቱ እጅግ ጠንካራና ረቂቅ ነው።

የታላቁ ሚስጢር ባላቤትና ባለውለታ የሆኑትን ትክሊላችን ካፒቴን ሻንበል ጉታ ዲንቃን ህይወት ከኢትዮጵያዊነት ሚስጢራዊ ተፈጥሮ ጋራ ከፍ ብሎ ዕውቅና እንዲያገኝ የነበረው ፍላጎትና ጉጉት ውስጡን ገልጦ ያሳይ ነበር ንግግሩ። ያን ቀን አባ መላ ዓዋጅም ዓወጆ ነበር  ከእንግዲህ አለ … “ልጅ የምትወልዱ ቤተሰቦች ልጆቻችሁን ጉታ ዲንቃ እያላችሁ ጥሩ“ አለ። የዛሬ ሳምንት ደግሞ „ ኢትዮጵያዊነት መሪ አገኘ ጉታ ዲንቃን“ አለን።

የካፒቴን ጉታ ዲንቃ ህልም ደቡብ አፍሪካ ሄዶ የምህረት፤ የትግል፤ የጽናት፤ የይበቃኛል አባት ከሆኑት ከኔልሰን ማንዴላ ቀብር ላይ መገኘት ስለነበር። የማይቻለውን ቻለ። በአራት ቀን ውስጥ ከኢትዮጵውያን የሚሰበሰበወን ገንዘብ ሳይጠብቅ የራሱን ገንዘብ የትኬት ምግዣ ልኮ። የኢሳትን ቲም፤ አርቲስት ታማኝ በዬነን፤ አቶ ነዓምን ዘለቀን በመያዝ በንዑድ ቅንነት ተግባሩን ጀመረ። በሩሙ ታዳሚዎች በመተማመን። ያው በፍቅር ስለሚያስተናግድ ለፍቅሩ የሚቻለውን ዋጋ ለመክፈል የቻሉ፣ በወቅቱ መልዕክቱን ያደመጡ፣ እንደ አቅማቸው ተባበሩት። ሀገር ውስጥም ደቡብ አፍሪካም የነበረውን ትብትቡን ቢሮክራሲ በታታሪንት ተቋቁሞ የዛሬ ሳምንት ዕለተ ቅዳሜ 14.12.2013 ዘውዳችን ሻንበል ጉታ ዲንቃ አውሮፕላን ውስጥ እንዳሉ ሲነገረን ፈነጠዝን። ዛሬ እኛነታችን፤ ማንነታችን ፈተና ላይ ወድቆ፤ ባለቤት አጥቶ ወገኖቻችን በዬተሰደደበት እያታነቁ በሚገደሉበት ወቅት አጋጣሚው የሰማይ ገድል ነበር። ሊያመልጠን አይገባም ነበር። በተባረኩ ወገኖችም አጋጣሚው እነሆ አፈራ። ቀሪው የሎቢ ተግባር ተጠናክሮ ከተሰራበት የበለጠ ትርፋማ መሆን ይቻላል። ኢትዮጵያዊነት የተከበረ ሰንደቅ ስለመሆኑ የዓለም ሚዲያ እንደመሰክር ማደረግ ይቻላል።

የተከበሩ ሻንበል ጉታ ዲንቃ ደቡብ አፍሪካ ከደረሱበት እስከ ተመለሱበት ድረስም የደቡብ አፍሪካ ጥቁር አንባሶች የኢትዮጵያዊነት ዓርማ ናቸውና አደራቸውን በተግባር አቅልመው ኢትዮጵያዊነትን ከፍ አደረጉልን። እግዚአብሄር ይስጣችሁ። በ2013 የአፍሪካ የእግር ኳስ ዋንጫ ወቅት ኢሮ ስፖርት ደቡብ አፍሪካ ላይ ስለሚገኙት ኢትዮጵውያን ልክ እንደ ሀገሩ ዜጋ ነበር በክብር ሲገልጻቸው የነበረው። ያኮራሉና! ኢሮ ስፖርት ስለ ኢትዮጵውያን የዘገበው እጅግ ነፍስን የሚገዛ ነበረ። ዛሬም ታሪካዊ ኃላፊነተቸውን በብቃት ተወጡ ሁነኛዎቻችን መካታና መመኪያዎቻችን ናቸው። ጠቅላላ ቃለ ምልልሱ፤ ምን እንደ ተሳማቸው ምስጋናው ሁሉም አለ …. ያልነባራችሁ ሲቢሊቲ ሩም እንሆ …. የ22.12.2013 የካፒቴን ሻንበል ጉታ ዲንቃ ቃለ ምልልስ በሲብሊቲ ሩም … „ፓን አፍሪካኒሰት የዘመኑ“ ይላቸዋል አባ መላ። በ አስር እጣታችን እንፈርማለን …. ጧፋችን ….

ማጠቃለያ …. አረሙ ወያኔ የምታሴሩትን የልዩነት ትብትብ ኢትዮጵውያን ፈተን አንድ ቀን ኢትዮጵያ ወደ ነበረችበት ክብር ትመለሳላች። በዚህ መልክ በትግባር፣ በመደማመጥ፣ ከተጋን አትጠራጠሩ የቀን ጉዳይ ነው። ከዚህ በተጨማሪ አሁንም የታሪካችን ሚስጢር አካል የሆኑት የጄ/ታደሰ ብሩ ልጆች ቤተሰቦች ይኖራሉ። እነሱን አፈለልጎ የተገባውን ክብር መስጠት የተገባ ነው። ከዚህ በተጨማሪም የማዲባ የቅርብ ጓደኛቸውና መምህራቸው የነበሩት ዛሬ ህመም ላይ ያሉት የኮ/ ፈቃደንም ጉዳይ የአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው ራዲዮ ያደረገው ቃለ ምልልስ በተጠናከረ ሁኔታ ቀጥሎ ትውልዱ ታሪኩን በአግባቡ ይዘግበው ዘንድ ዝቅ ብዬ አሳስባለሁ። አክብሮታችን ፍለጋችን እኩል በተግባር ደምቆ መከናወን አለበት። ኢትዮጵያዊነትም ወደ ዘውዱ።

ዛሬ ደግሞ አባ መላ አዲስ ሃሳብ ይዞ መጥቷል ከትንሹ እንጀምር እያለን ነው። ወያኔ ለእርቅ ጠርቶ  እስርና ለበሸታ የዳረጋቸውን ጽኑ አቶ አበራ የማናአብ ከቤተሰባቸው ጋር አሜሪካን ሀገር የማቀላቀሉ የሎቢ ተግባር አብረን እንታደም ዘንድ አሳስቦናል። ወያኔ የሚጠላውን ስንፈጽም ወያኔን በቁሙ መግደል እንችላለን። ለነጻነት የአንድ ወጣት ዕድሜን ያሳለፉ፤ በሳንባ በሽታ የተጠቁ አካላችነን በአክብሮት ማገዝ በመርዳት ከጎን ተሰልፎ የድርሻን መወጣት ይገባል – ከትህትና ጋር። ቃለ ምልልሱ፤ ምን እንደ ተሳማቸው ምስጋናው ሁሉም አለ …. ያልነባራችሁ ሲቢሊቲ ሩም እንሆ …. የ22.12.2013 የካፒቴን ሻንበል ጉታ ዲንቃ ቃለ ምልልስ በሲብሊቲ ሩም … „ፓን አፍሪካኒሰት የዘመኑ“ ይላቸዋል አባ መላ። በ አስር እጣታችን እንፈርማለን …. ጧፋችን …. ልብል እኔ ደግሞ

 

ኢትዮጵያ ለዘለ ዓለም ትኑር!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ

 

ፍርድ ቤቱ አንድነት በኢቴቪ ላቀረበው ክስ ውሳኔ መስጠት ተስኖታል

$
0
0

ዳዊት ሰለሞን
መስከረም 3/2004 የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግኑኝነት ሀላETVፊ የሆነውን አንዷለም አራጌ፣የብሄራዊ ምክር ቤት አባሉን ናትናኤል መኮንንና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በቁጥጥር ስር መዋላቸው አይዘነጋም፡፡መንግስት ተጠርጣሪዎቹን ካሰረ በኋላ አሁን በህይወት የሌሉት መለስ ዜናዊ በፓርላማ‹‹ማስረጃም መረጃም አለን››በማለት እነአንዷለም ሽብርተኞች ስለመሆናቸው በድፍረት መናገራቸው ይታወሳል፡፡
ኢቴቪም ከጸረ ሽብር ግብረ ሀይል ጋር በመተባበር መለስ የፎከሩበትን መረጃና ማስረጃ ‹‹አኬልዳማ››በሚል ርዕስ ለማሳየት መዘጋጀቱን አታሞ መጎሰም ጀመረ፡፡አኬልዳማ ተጠርጣሪዎቹን ከፍርድ ቤት በፊት በሽብርተኝነት የወነጀለ፣ፓርቲውን ከሽብርተኛ ተቋማት ጋር ጋብቻ እንደፈጸመ አድርጎ በተራ ውንጀላ የፈረጀና የአንድነት አባላት ያልሆኑ ሰዎችን አባላት በማድረግ ያቀረበ የተለመደው ማጥላላት፣ሴራና ውሸት በመሆኑ ፓርቲው ለኢቴቪ አቤቱታ በማቅረብ እርምት እንዲወሰድ ይጠይቃል፡፡የኢቴቪ ቦርድ አመራሮች ግን ለዚህ ጆሮ አልነበራቸውምና፡፡በጥር 2004 ፓርቲው ክሱን አቀረበ፡፡
የፓርቲው ጠበቆች በቢፒአር መታየት ይገባዋል በማለት በፍጥነት እንዲታይላቸው ያቀረቡት ክስ እነሆ እስካሁን ድረስ ውሳኔ ሳያገኝ በድጋሜ ለጥር ወር ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡ለ20ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረበው ክሱ በጥር ወር ሁለተኛ አመቱን ይደፍናል፡፡

የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን በዣንጥላና በምንጣፍ መለመንን ከልክላ በካሽ ርጅስተር ተጠቃሚ ልትሆን ነው

$
0
0

ቅዳሜ ዕለት የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንዘገበው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ በዣንጥላና በምንጣፍ መለመንን ከልክላ በካሽ ርጅስተር ልትጠቀም መሆኑን ዘግቧል። ጋዜጣው ጨምሮም ምእመናን ለቤ.ክ ሲሰጡ ደረሰኝ የሚጠይቁበት አሰራር ይኖራል ብሏል።

የአዲስ አድማስ ሙሉ ዘገባ እንደሚከተለው ነው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማት፣ አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት የካሽ ሬጅስተር ማሽንን ለገቢ መሰብሰቢያነት ለመጠቀም የሚያስችላቸው ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መኾኑ ተገለጸ፡፡

ዘመኑን ያልዋጀውንና ጥራት የጎደለውን፣ ለሙስናና ብክነት የተጋለጠውን የቤተ ክርስቲያኒቱን የፋይናንስ አሠራርና ቁጥጥር ችግር ግልጽነት፣ ወጥነት፣ ተቀባይነትና ተጠያቂነት ባለው የፋይናንስ አያያዝ ሥርዐት ለመቅረፍና ለማድረቅ ያስችላል፤ በሚል በቀረበው የሀገረ ስብከቱ የሒሳብ አያያዝ ፖሊሲና ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ ረቂቅ ላይ እንደተጠቀሰው÷ በማንኛውም መንገድ የተሰበሰበ ገቢ ገንዘብ ሕጋዊ የገቢ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ወዲያውኑ ሊቆረጥለት የሚገባ ሲኾን ይህም በዋናነት በካሽ ሬጅስትር ማሽን እንደሚከናወን ተመልክቷል፡፡
bole_church_ethiopia-300x225 (1)
የሀ/ስብከቱ አብያተ ክርስቲያናት የካሽ ሬጅስተር ማሽን ተጠቃሚ መኾናቸው በገቢ ሒሳብ አሠራርና ቁጥጥር እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ለመከላከል ያስችላል፡፡ በጥናቱ ላይ በመነሻነት ከተዘረዘሩት ችግሮች ለመረዳት እንደሚቻለው በዕለት ገቢዎችና ደረሰኝ አጠቃቀም ረገድ፡- የቤተ ክርስቲያኒቱን የገንዘብ ገቢ ሰነዶች በሕገ ወጥ መንገድ አሳትሞ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም ለግል ገንዘብ ይሰበሰባል፤ በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የተከለከለ ደረሰኝ ጥቅም ላይ የሚውልበት አጋጣሚ ታይቷል፤ ከደረሰኙ በበራሪው/ለከፋዩ ከሚሰጠው/ የተለየ መጠን በቀሪው ላይ መጻፍና የግል ጥቅምን ማካበት ይዘወተራል፤ በዘወትርና በክብረ በዓላት በርካታ ገንዘብ ገቢ ቢኾንም በዕለቱ ወደ ባንክ ያለማስገባት ኹኔታ አለ፤ ምእመናን ለሚከፍሉትና ለሚሰጡት ገንዘብ ከመተማመን አንጻር ደረሰኝ የመቀበል ልማድ የለሌላቸው መኾኑን እንደክፍተት በመጠቀም ለቤተ ክርስቲያን የመጣው ገንዘብ ‹‹በየመንገዱ እየተንጠባጠበ ወፎች የሚለቃቅሙት ይበዛል፤›› በሥራ ላይ ያልዋሉ የገንዘብ ገቢና ወጪ ሰነዶች (ሞዴላሞዴሎች ሴሪ ንምራ ቁጥር) መሠረታዊ ችግር ተጠንቶ መፍትሔ አልተሰጠም፡፡

በንግሥ፣ በወርኃዊ በዓላትና በዕለተ ሰንበት በሙዳየ ምጽዋት ሳይኾን በተዘረጋ ጨርቅ ላይ የሚሰበሰብ ገንዘብ መኖሩን የሚጠቅሰው ጥናቱ÷ በዚህ መልክ የተሰበሰበው ገንዘብ ሀ/ስብከቱ በታኅሣሥ፣ 2003 ዓ.ም. ባስተላለፈው የገንዘብ ቆጠራ፣ የንብረት አመዘጋገብና አጠባበቅ የሥራ መመሪያ መሠረት የምእመናንና ካህናት ሰበካ ጉባኤ ተወካዮች በሙሉ በተገኙበት ቆጠራ የማይካሄድበትና በተወሰነ መልኩም ሙሉ ገንዘቡ ገቢ የማይደረግበት ኹኔታ በመኖሩ አሠራሩ ለብኩንነት፣ ሐሜትና አሉባልታ መጋለጡን ገልጧል፡፡ በንግሥ በዓላት ወቅት ጥላ ዘቅዝቀው የሚለምኑ ሰዎች ኹሉም ስለማይታወቁ የተኣማኒነት ችግር አለ፡፡ በስእለትና በሙዳየ ምጽዋት በውጭ ምንዛሬ የሚገቡ የውጭ ሀገር ገንዘቦች በመመሪያው መሠረት በዕለቱ የባንክ ምንዛሬ ወደ ብር እየተቀየሩ በተገቢው መንገድ ገቢ አለመኾናቸው፣ በምትኩ ቅያሬው ወጥነት ያለውና ለብኩንነት የተጋለጠ እንደኾነም ተዘግቧል፡፡

በቃለ ዐዋዲ ድንጋጌው የተመለከተውንና በዝርዝር የሥራ መመሪያ የተላለፈውን የገቢ አሰባሰብ በተሻለ አሠራር ያጠናክራል የተባለው በፖሊሲና መመሪያ ረቂቁ የሒሳብ ሰነዶች አያያዝ፣ ምዝገባና አወጋገድ መሠረት÷ ለሒሳብ ሥራ የሚያገለግሉ ደረሰኞችና ቫውቸሮች የዋና ተጠቃሚውን ተቋም ስም ይዘው በሀገረ ስብከቱ ምስጢራዊ ኮድ ይዘው ይታተማሉ፤ የማሳተም ሓላፊነቱም የሀገረ ስብከቱ የፋይናንስና በጀት ዋና ክፍል ሲኾን ይህም በዋና ሥራ አስኪያጁ ፈቃጅነት የሚከናወን ይኾናል፡፡Cash register machine

በማንኛውም መንገድ የተሰበሰበ ገቢ ሕጋዊ የገንዘብ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ወዲያውኑ ሊቆረጥለት ይገባል፤ ይህም በዋናነት በካሽ ሬጅስተር ማሽን ተፈጻሚ ይኾናል፤ የገንዘብ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ከገንዘብ ሰብሳቢ ውጭ መያዝና መጠቀም አይቻልም፡፡ ማንኛውም የገንዘብ ስጦታ በገንዘብ ያዡ በኩል መሰጠት ይኖርበታል፤ ስጦታው እንደተበረከተም ወዲያውኑ የገንዘብ መቀበያ ደረሰኝ ሊቆረጥለት ይገባል፡፡ በዐይነት የሚሰጥ ስጦታ በግዥ፣ ሽያጭና ንብረት አስተዳደር ፖሊሲና ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ መሠረት በተተመነለት ዋጋ ይመዘገባል፡፡
cash rigestor
ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ውጭ በሙዳየ ምጽዋት ሣጥን ገንዘብ መሰብሰብ አይቻልም፤ ቋሚ ሙዳየ ምጽዋት በቅጽረ ቤተ ክርስቲያን የሚቀመጥበት ቦታ ተጠንቶ በሰበካ ጉባኤው መጽድቅ አለበት፤ ለቆጠራ ካልኾነ በቀር ከተቀመጠበት ማንቀሳቀስ አይቻልም፤ በትከሻና ተይዘው የሚዞሩ ሙዳየ ምጽዋት ሣጥኖች ሙሉ መረጃ ተመዝግቦ ይያዛል፡፡ የሙዳየ ምጽዋት ቆጠራ በሚካሄድበት ወቅት ሣጥኖቹ ከመከፈታቸው በፊት ሁሉም ቆጣሪዎች የቁልፍ ካዝናውና የቁልፍ ሣጥኖች፣ የሣጥኖቹን ብዛትና እሽጋቸው አለመከፈቱን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል፤ የተቆጠረ ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ወዲያውኑ ካልተቻለ ከሌላ ገንዘብ ጋራ ሳይቀላቀል በበነጋው ወደ ባንክ አካውንት መግባት አለበት፤ ዣንጥላን፣ ምንጣፍንና የመሳሰሉትን በመጠቀም ገንዘብ መሰብሰብ ፈጽሞ የተከለከለ ይኾናል፡፡

[የሀገረ ስብከቱ የመዋቅርና አደረጃጀት ሰነድ አካል የኾነው የሒሳብ አያያዝ ፖሊሲና ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ ጥናት ረቂቅ እንደሚያትተው÷ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት፣ የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቶች፣ የልማትና በጎ አድራጎት ተቋማት፣ ደረጃ አንድ እና ሁለት የኾኑ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በኮምፒዩተር የታገዘ የሒሳብ አያያዝ ዘዴን/ሥርዐት እንዲከተሉ ይደረጋል፡፡ የሒሳብ አያያዝ ዘዴውም የሁለትዮሽ የሒሳብ አያያዝ ዘዴ(Double entry system) ሲኾን በአክሩዋል ቤዝስ ከሚጠቀሙት ከልማት ተቋማት በስተቀር የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትና በሥሩ ያሉ ሌሎች ተቋማት በጥሬ ገንዘብ ላይ የተመሠረተ፣ ገቢንና ተከፋይን በታሳቢነት በሚያስላው የሒሳብ አያያዝ ዘዴ(Modified cash bases) እንዲከተሉ ለማድረግ መታቀዱ ተገልጦአል፡፡ በኮምፒዩተር የሚታገዘው የሒሳብ አያያዝ ሶፍትዌርም በሀገረ ስብከቱ ተመርጦ የተዘጋጀው እንደሚኾን ታውቋል፡፡

የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዕውቀትና ዘመናዊው የፋይናንስ ሞያ በጥምረት ሥራ ላይ ለሚውልበት ለዚህ አሠራር ተፈጻሚነት÷ ከሀገረ ስብከቱ፣ ከክፍለ ከተማ ጽ/ቤቶችና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ተመርጠው ለተውጣጡና ለሚመለከታቸው የሒሳብና የቁጥጥር ሓላፊዎችና ሠራተኞች ሥልጠና እንደሚሰጥ የተጠቆመ ሲኾን የሀገረ ስብከቱ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና ዶኩመንቴሽን ዋና ክፍል በማእከል ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠረው የመሠረተ - ቴክኖሎጂው ዝርጋታ በሚተገበርባቸው ተቋማትና አብያተ ክርስቲያናትም በግልጽ የፕሮጀክት አሠራር እንደሚፈጸም ተገልጧል፡፡]
ዘመናዊው የፋይናንስ አሠራር በሀገረ ስብከቱ ተቋማትና አብያተ ክርስቲያናት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሲኾንም በተጭበረበሩ ደረሰኞችና በማይታወቁ የገንዘብ አሰባሰቦች የግል ጥቅምን ማካበት በመከላከል ለክትትልና ቁጥጥር አመች ለማድረግ እንደሚያበቃ ተመልክቷል፡፡ በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት፣ በልማትና በጎ አድራጎት ተቋማቱ እንዲሁም በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናቱ የሚዘጋጁ የፋይናንስ ሪፖርቶች ግልጽነት፣ ወቅታዊነትና ተኣማኒነት/ተቀባይነት እንዲኖራቸው ለማድረግ፣ ሀገረ ስብከቱ በሚሰበሰበው የኻያ በመቶ ፈሰስና ከአብያተ ክርስቲያናቱ በቅጽ ተሞልቶ በሚላከው ሒሳብ መካከል በየዓመቱ የሚያጋጥመውን ልዩነት ለማስወገድ እንደሚያስችል ተገልጧል፡፡

ይህም በሒደት ከፍተኛ የሀብት ክምችት የሚገኝበት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በፋይናንስ አሠራሩና መልካም አስተዳደሩ የሁሉም አህጉረ ስብከት ሞዴል በመኾን ቤተ ክርስቲያኒቱ በመንበረ ፓትርያርክ ደረጃ ማእከላዊ የፋይናንስና በጀት አስተዳደር ይኖራት ዘንድ መሠረት ለመጣል፣ የካህናቷን ኑሮ በማሳደግና በማሻሻል ሐዋርያ ተልእኮዋን ለማጠናከር ከፍተኛ አቅም የምትፈጥርበት መሠረት ለመጣል እንደሚያስችላት ታምኖበታል፡፡

በሳዑዲ አረቢያ ዛሬ የተነሳው የሸሜሲ መጠለያ ሁከት እልባት ሳያገኝ ቀረ

$
0
0

በሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በፌስቡክ ገጹ እንደዘገበው፦
የዛሬው የሽሜሲ መጠለያ ሁከት …

የጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ” ህጋዊ ሰነድ የማታሟሉ ወደ ሃገር ቤት ግቡ! ” ያወጣውን ተደጋጋሚ መረጃ ተከትሎ ከአምስት ቀናት ጅምሮ ወደ ሽሜሲ መጠለያ በአስር አውቶቡስ በላይ ሆነው የገቡ ኢትዮጵያውያን ሜዳ ላይ ተጥለው ለከፋ መጉላላት መዳረጋቸው ገልጸዋል። አኒሁ ቅሬታ አቅራቢ ዜጎች በማከልም የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ዛሬ ጠዋት ሊያነጋግሯቸው የመጡ ቢሆንም ” ተረጋጉ እንመለሳለን !” ብልዋቸው መፍትሄ ሳይሰጧቸው እንደሄዱ ገልጸውልኛል። የሃላፊዎች ሙሉ ቀን መጥፋት ያበሳጫቸው ነዋሪዎች ዛሬ ከቀትር በኋላ በነፍሰ ጡር ፣ በህጻናት ላይ እያደረሰ ያለውን መንገላታት እየጎዳቸው መሆኑን በመግለጽ ለሳውዲ ሃላፊዎችን መፍትሔ ቢጠይቁም ” መፍትሄው በእናንተ ሃላፊዎች እጅ እንጅ ፣ በእኛ እጅ አይደለም! ” በማለት እንደመለሱልቸው እና ነዋሪው በብስጭት አስወጡን በሚል ወደ በሮች ቢጠጋም በወታደሮች መከልከላቸው በምሬት ገልጸውልኛል። ለሶስት ሰአታት በመጠለያው ውስጥ በተከሰተው ተቃውሞ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ጉዳዩን አሳሳቢነት በመረዳት ወደ ቦታው በመሄድ ነዋሪውን አለማረጋጋታቸውን ብዙዎችን አሳዝኗል ።

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)


ዛሬ በሽሜሲ መጠለያ የተነሳው ግርግር መንስኤነት በጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች እና በሳውዲ የመጠለያው ከፍተኛ ሃላፊዎች ጋር በተከሰተ አለመግባባት እንደሆነ ጉዳዩን ለማጣራት ባደረጉት ሙከራ ለመረዳት ችያለሁ! የአለመግባባቱ ምንጭም መኖሪያ ፍቃዳቸውን ጥለው ወደ ሃገር የሚገቡ ዜጎችን ሰነድ ማጓተት ተከትሎ የቆንስል ሃላፊዎች ” ወደ ሃገር መግባት የሚፈልጉ ዜጎቻችን የመውጫ ሰነድ እስካልተሰጠ ድረስ ሰነድ አንሰራም!” አስገዳጅና ጠቃሚ መከራከሪያ በማቅረባቸው እንደሆነ ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ! ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ስልክ በመደወል ያደረግኩት ሙከራ አልተሳካም ።

የሽሜሲ ተቃውሞ እልባት ሳያገኝ በዚህ መልኩ ከቀጠለ እና ነዋሪዎች በሁኔታው ተማረው በሚወስዱት ተቃውሞ ለረብሻና ሁከት ሰበብ እንዳይሆን ሊታሰብበት የሚገባ ሲሆን ነዋሪውም ምግብና ውሃ በአግባቡ እስከ ቀረበ ድረስ ጉዳዩን በትዕግስት ሊጠባበቁ እንደሚገባ ይመከራል! በተመሳሳይ ሁኔታ ወደ ሃገር እንግባ በሚል በግላቸው ወደ ሽሜሲ መጠለያ የሄዱት በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎችም በመጠለያው በት በመጉላላት ላይ መሆናቸውን ገልጸውልኛል። አቤቱታቸውን በተደጋጋሚ ያቀረቡልኝ ነዋሪዎች እኔን ሳይቀር “ድምጻችን አታፍንብን ፣ ለአለም አሰማልን! “ሲሉ ሃይለ ቃልን ጨምረው ወቅሰውኛል !

ቸር ያሰማን

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ለዳግመኛ ክህደት እንዳይደረግ ሲሉ የቀድሞ አየር ኃይል አባላት ወቅታዊ ጽሁፍ በተኑ

$
0
0

የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል አባላት በወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ በመመርኮስ “በደም የተገነባ ተቋም” በሚል በበተኑት ጽሁፍ የአየር ኃይል ለዳግመኛ ክህደት እንዳይበተን ሲሉ አሳስበዋል። ለዘ-ሐበሻ የደረሰው የቀድሞው አየር ኃይል አባላት ጽሁፍ እንደሚከተለው ተስተናግዷል።
ethiopian airforce
በደም የተገነባ ተቋም
የኢትዮጵያ አየር ኃይል
(ለዳግመኛ ክህደት እንዳይዳረግ)

ግንቦት 83/91 ላይ የኢትዮጵያ ሰማይ ክፉኛ በሃዘን ሲመታ ፣ ደመናው ሲጠለሽ ፤ ወንዞች መደፈራረስ ሲጀምሩ፤ የሰውን ልብ ባር ባር ሲለው …….. የክፉው ቀን ጅማሮ ፣ የውርደት ሃሌታ ፣ የሃገር አልባነት ስሜትና የዜግነት ውርደት ደጃፍ ላይ መውደቃችን እውነት ነበር ።
ውርስ ከአባት ወደ ልጅ ሊተላለፍ ካልቻለ ፤ አባት የጀመረውን ልጅ ካልቋጨው ፤ አዲስ መንግስት ሲቀየር የድሮውን በጐ ነገር ሁሉ ብትንትኑን አውጥቶ ካጠፋ ፤ የትውልድ ቅብብሎሽ ገደል ገባ ማለት አይደል ? እናም በአገሬ ምድር ላይ የእርግማን ዘመን ያኔ “ በ1991 “ “ ሀ “ ብሎ ጀመረ ።
ሌባው ከሳሽ … ቀማኛው ፈራጅ የሆነበት ፤ አባት ተቀምጦ ልጅ የሁሉ ነገር አዛዥ ሲሆን ፤ አህያ ወደ ሊጥ … ውሻም ወደ ግጦሽ ከተሰማራ …. እነሆ ዘመነ ብልሹ ላይ መድረሱን ያልተረዳ ካለ … እሱ ባይፈጠር …. እናቱ ሆድ ውስጥ ውሃ ሆኖ ቢቀር ይሻለው ነበር ።

ሙሉውን ዘገባ በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ዝነኛው አርቲስት ቴዎድሮስ ምትኩ አረፈ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) አርብ ሴፕቴምበር 7 ቀን 2013 ታዋቂው የሙዚቃ ሰው ቴዲ (ቴዎድሮስ) ምትኩ በሜሪላንድ ግዛት ሆስፒታል መግባቱ ተገለጸ በሚል ዘ-ሐበሻ ዘግባ ነበር። ይህ ዜና እንደተሰማም በርካታ የኢትዮጵያ ሙዚቃ አፍቃሪያን ይህን ዝነኛ አርቲስት ፈጣሪ ምህረቱን እንዲሰጠው ሲጸልዩ ቆይተው ድምጻዊው ከሆስፒታል ተሽሎት ወጣ።

ሆኖም ግን ዛሬ ጠዋት ዲሴምበር 22 ቀን 2013 ዓ.ም 4፡06 ላይ ኢትዮጵያውያንን ከ1960ዎቹ ጀምሮ ሲያዝናና የነበረው ቴዎድሮስ ምትኩ ማረፉ ተሰምቷል። የድምጻዊው የቀብር ቦታ እና የፍትሃት ሁኔታው ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ባይሰማም፤ የፊታችን ማክሰኞ ሊሆን ይችላል የሚል መረጃ ግን ለዘ-ሐበሻ ደርሷል። ሁኔታውን ተከታትለን እንዘግባለን።

ዝነኛው ቴዎድሮስ ምትኩ የጥላሁን ገሰሰ ባለቤት እህት ከሆነችው ወ/ሮ መአዛ በዙ ጋር ላለፉት 22 ዓመታት በትዳር ዓለም ቆይቷል።

ዘ-ሐበሻ በዚህ ታዋቂ የሳክስፎን ባለሙያ የተሰማትን ሃዘን እየገለጸች ታዋቂው ጸሐፊ ዳግላስ ጴጥሮስ እንደ አርቲስት ቴዎድሮስ ምትኩ ያሉ ዝነኞችን ለማስታወስ የጻፈውን ለግንዛቤ አስተናግዳለች።
ከዳግላስ ጴጥሮስ
የአንድ ጐልማሳ ዕድሜን ያህል ወደ ኋላ ዞር እንድንል የዛሬው ርዕሰ ጉዳዬ ትዝታ ይቀሰቅሳል – ከ1960ዎቹ ዓመታት በፊት፡፡ በእነዚያ ዓመታት ውስጥ በትምህርት ቤቶቻችን ውስጥ በድንቅ ባህልነቱ የሚጠቀስ አንድ ጥበብ በተለየ ሁኔታ አብቦ ነበር፡፡ ያውም የሙዚቃ ጥበብ፡፡
ይሁን እንጂ ይህን መሰሉ ባህል ከዘመን ዘመን የሚሸጋገር ፍሬ እንዳያፈራ «የሥርዓቶች ዋግ መትቶት» በአበባ ብቻ ሊቀር ግድ ሆኗል፡፡ በጭንገፋ ተመትቶ «ግባ መሬቱ» የተፈፀመው ይህ የጥበብ ቡቃያ ፍሬው ከትውልድ ትውልድ እንዳይተላለፍ በእሸትነቱ ስለ ተቀጨ እነሆ የዛሬው ጥበብ ነክ ችግራችን ገዝፎና ሥር ሰዶ «ለወይነዶ!» ቁጭት ዳርጎናል፡፡
ዝነኛው አርቲስት ቴዎድሮስ ምትኩ አረፈ
«ዛሬ» የሚለው ቃል በጽሑፌ ውስጥ መደጋገሙ አለብልሃት አይደለምና አንባብያን እንድትታገሱኝ በመቅድም አቤቱታ እማፀናለሁ፡፡
እናም የዛሬን አያድርገውና ለልዩ ልዩ ሕዝባዊ ክብረ በዓላት በመዲናችን አዲስ አበባና በዋና ዋና የሀገራችን ከተሞች በዓላቱን የሚያደምቁት የማርች ባንድ (በተለምዶ ማርሽ ባንድ የሚባለው) ሙዚቀኞች ከወታደራዊ ክፍሎች የተገኙት ብቻ አልነበሩም፡፡ ከእነርሱ ባልተናነሰ ደረጃ ያውም በተሟላ ዘመናዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ተደራጅተውና ማራኪ የደንብ ልብስ ለብሰው ጥዑም ዜማቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡ የትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንዶች ያበቡበት ወቅት ነበር፡፡ ወጣትነት በለገሳቸው መለሎ ቁመት እየተውረገረጉ የተመልካችን ቀልብ ይስቡ የነበሩት እኒያ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ታዳጊ የሙዚቃ ጠበብት ዘግይቶ በተፈጠረው ትውልድ ይዘነጉ ካልሆነ በስተቀር በታሪክ መዝገብ ውስጥ ግን ህያው እንደሆኑ መቆየታቸውን የሚደልዝ የተሟጋች ብዕር አይኖርም፡፡
ዳግማዊ ምኒልክን፣ ኰከበ ጽባሕን፣ የደሴው ወ/ሮ ስሂንና የናዝሬቱን አፄ ገላውዲዎስ ትምህርት ቤቶች ብቻ ለጊዜው በክብር ልዘክር፡፡ እነዚያ ትምህርት ቤቶች የነበራቸው የሙዚቃ ባንዶች (ኦርኬስትራና ማርቺንግ ባንድ) በወቅቱ ለተደረሰበት የሙዚቃ ዕድገት ከፍታ ብቻ ሳይሆን በእነዚያ የሙዚቃ ባንዶች ውስጥ ተፈጥረው፣ አድገውና በጥበቡ ተራቅቀው ከሙዚቃ ጋር ነፍስና ሥጋቸው እንደተቆራኘ የሚገኙ ባለሙያዎች ቁጥር ቀላል የሚሰኝ አይደለም፡፡ ሌሎቹን ጥበባት ወቅትና ጊዜ ሲፈቅድ አስታውሳቸዋለሁ፡፡
«ክርስቶስ ለሥጋው አደላ” እንዲሉ የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ዕውቀት የተጐነጨበትን የዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንድ የሚያስታውሰው በትልቅ አክብሮት ነው፡፡ ልዩ ልዩ ክበረ በዓላት ሲመጡ አዲስ የሙዚቃ ቅንብር ለመፍጠር ቀን ከሌት ይደረግ የነበረው ኃላፊነት የተሞላበት የተማሪ ጓደኞቹ የሸብ ረብ ዝግጅት አስደናቂ የሚሰኝ ብቻ ሳይሆን ከግምት በላይ ሊነገርለት የሚገባ ነው፡፡ በወርቃማ ጐፈርና በቀይና ቢጫ ቀለማት የተዋበው የተማሪዎቹ የሙዚቃ ባንድ ገና የትምህርት ቤቱን በር አልፎ ወደ ዋናው የአራት ኪሎ አውራ ጐዳና ሲገባ በዕልልታ ይቀርብለት የነበረው የሕዝብ አቀባበል ወደር አልነበረውም፡፡ በዚህ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንዶች ውስጥ ያገለግሉ የነበሩት የያን ጊዜዎቹ ተማሪዎች በኋለኞቹ የጉልምስና ዕድሜያቸው ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ዕድገት የተጫወቱት ሚና እንዲህ በዋዛ በቀላል የሃሳብ ጥቅሻ የሚታለፍ ስላይደለ ጥቂቶቹን ብቻ ለአብነት በመጥቀስ ዝርዝሩን በይደር ማስተላለፉ ይበጃል፡፡

ወደ ኰከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት እስኪዛወር ድረስ የዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት ማርቺንግ ባንድ ታንቡር መች የነበረው የሙዚቃው ሊቅ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደና በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ውስጥ ከከፍተኛ የሥራ መሪነት እስከ መምህርነት እያገለገለ የሚገኘው አቶ ሰሎሞን ሉሉን ብቻ ለአብነት አስታውሼ ልልፍ፡፡ አቶ ሰሎሞን ሉሉ አሁን በሥራ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሔራዊ መዝሙር የዜማ ደራሲ እንደሆነም ማስታወሱ አስፈላጊ ነው፡፡
እኒህን መሰል ጐምቱ የሙዚቃ ጠበብት ተኰትኩተው ያደጉት በአንጋፋው የዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንድ ውስጥ ነው፡፡ እኒህንና ሌሎች በርካታ ወጣቶችን ሲያሰለጥኑ የነበሩት አቶ ዘውዱና አቶ መብራቱም የማይዘነጉ የጥበቡ ፊታውራሪዎች ነበሩ፡፡
የኰከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንድም ልክ እንደ ትምህርት ቤቱ ስም ሁሉ በወቅቱ የፈካ አጥቢያ ኰከብ ነበር፡፡ በዚያ የሙዚቃ ባንድ ውስጥ አድገው የወጡት ወጣቶችም በሀገራችን የሙዚቃና የቴአትር ጥበብ ላይ ያሳረፉት በጐ አሻራ ሊዘነጋ ከቶውንም አይችልም፡፡ ጥቂቱቹን ልዘክር፡፡ የትምህርት ቤቱ ዘንግ ወርዋሪ፣ ትራንፔት ተጫዋችና ድምፃዊ የነበረው ዓለሙ ገብረአብ እንዴት ይረሳል፡፡ ዓለሙ ገብረአብ ሕይወቱ እስካለፈ ጊዜ ድረስ የብሔራዊ ቴአትር ቤት ፈርጥ ተዋናይ ነበር፡፡
ዛሬ በውጭ ሀገራት ኑሮአቸውን የመሠረቱት ዝነኞቹ የሙዚቃ ባለሙያ ወንድማማቾቹ ተሾመ ምትኩና ቴዎድሮስ ምትኩ የኰከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንድ አባላት ነበሩ፡፡ በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ከዲሬክተርነት እስከ መምህርነት የዘለቀው አቶ ተክለ ዮሐንስ ዝቄ የዚሁ ትምህርት ቤት ፍሬ ነው፡፡ ታምራት ፈረንጅ፣ ተስፋዬ መኰንን፣ ታምራት ሎቴ፣ ሞገስ ሀብቴ ብዙዎቹ በሕይወት ባይኖሩም በተነደፉበት የሙዚቃ ፍቅር እስከ መጨረሻ የዘለቁት የኰከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት ባንድ ከጥበቡ ፍቅር ጋር ስላቆራኛቸው ነበር፡፡ የእነዚህ ወጣቶች አሠልጣኝ የነበሩት አቶ ማሞ ደምሴና አቶ ጌታነህ ታደሰም አይዘነጉም፡፡ በምሥረታውና በማጠናከሩ ሂደት ላይ የጐላ ድርሻ የነበራቸው ዳኒሻዊውን ፓል ባንክ ሃንሰንን የመሳሰሉ የውጭ ሀገር መምህራንን ለጊዜው በማስታወስ ብቻ እናልፋቸዋለን፡፡
የዝነኛው የደሴው ወ/ሮ ስሂን ትምህርት ቤት የወጣቶች ፖለቲካዊና ሁለገብ ገናና ተሳትፎ በታሪክ የከበረ ቦታ እንዳለው አይደለም የሰው ምስክርነት ሣር ቅጠሉም ቢሆን እኔ ልናገር ብሎ ለዋቢነት መሽቀዳደሙ አይቀርም፡፡ በተለይ ግን የወ/ሮ ስሂን ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንድ በወቅቱ የነበሩትን ወታደራዊ የሙዚቃ ባንዶችን ብቃት በከፍተኛ ሁኔታ ይፈታተን እንደነበር ዕድሜውን የታደሉት ሁሉ የሚያስታውሱት ነው፡፡
የናዝሬቱ ዓፄ ገላውዲዎስ፣ የሐረሮቹ መድኃኒዓለም ትምህርት ቤት እና የመምህራን ማሠልጠኛ ተቋም የሙዚቃ ባንዶችም የነበራቸው ዝና እንዲሁ በጥቂት ቃላት እየታወሰ የሚታለፍ ባይሆንም ዝርዝሩን ለታሪክ ጸሐፍት በመተው ለዝክር ያህል ስማቸውን አስታውሰን እናልፋለን፡፡ የአዲስ አበባዎቹን መድኃኒዓለም ትምህርት ቤትና ተፈሪ መኰንን ትምህርት ቤትን በተመለከተ ግን ንባቤና መረጃዬ ስላልዳበረ እንዲህ ነበሩ ለማለት ድፍረት አጥቻለሁ፡፡ እነዚህን ሁለት ትምህርት ቤቶች በተመለከተ አዋቂዎች ቢያስተምሩን ነበርኩበት ባዮች ቢያሳውቁን ለዕውቀታችን በእጅጉ ይጠቅመናል፤ ከስህተትም ይታደገናል፡፡ መድኃኒዓለም ትምህርት ቤትን ካነሳሁ አይቀር ብዕረ መንገዴን በትምህርት ቤቱ ዋና መግቢያ ላይ ይነበብ የነበረውንና በፍፁም ከህሊናዬ ሊወጣ የማይችለውን ጥቅስ አስታውሼ ልለፍ፤ «ከዚህ ከማይሞተው የሰው ልጅ ማደጊያ ሥፍራ ግቡ» የሚለውን፡፡ ዛሬስ ያ ጥቅስ በቦታው ይገኝ ይሆን?
በውስን የጋዜጣ ገጽ ግዙፍ ሃሳቦችን ማስተናገድ ፈተናው የትዬለሌ መሆኑን አንባቢያን እንደሚረዱት ተስፋ በማድረግ ወደ ማጠቃለያው ሃሳብ ብዕሬን በፍጥነት ማንደርደሩን መርጫለሁ፡፡
ዛሬን ከቀዳሚ ዘመናት ጋር እያስተያዩ ይህ ጐደለ ይህ ሞላ ማለቱ አግባብ ባይሆንም ትናንትን ከዛሬ ጋር እያነፃፀሩ መልካሙን ማስታወሱ ግን ተገቢነት ይኖረዋል፡፡ ለምን ቢሉ፤ «ብልህ ከትናንት ይማራል፣ ሞኝ ግን ዕለት በዕለት ይሳሳታል» እንዲሉ መሆኑ ነው፡፡
ከላይ በተዘረዘሩት ትምህርት ቤቶች የሙዚቃ ባንድ ውስጥ አባላት የነበሩት ወጣት ተማሪዎች ትምህርት ቤታቸውን ከተሰናበቱ በኋላ ምን ሠሩ? ምን ፈፀሙ? ዛሬስ የት ናቸው? ተገቢ ጥያቄዎች ናቸው፡፡
በታዳጊነት ዕድሜ ከመደበኛው ትምህርታቸው ጐን ለጐን በሙዚቃ ፍቅር የወደቁት እኒያ ወጣቶች የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአሸናፊነት ተወጥተው በልዩ ልዩ ሙያቸው ለሀገራቸው ኩራት እንደነበሩና እንደሆኑ ሥራቸውና ስማቸው ምስክር ነው፡፡
ለአብነት ያህልም በዘመኑ ዝነኛ ባንድ የነበረውን «ሶል ኤኰስ» በመባል ይታወቅ የነበረውን ባንድ የመሠረቱት በኰከበ ጽባሕ የሙዚቃ ባንድ ውስጥ የነበሩት ተስፋዬ (ሆዶ) መኰንን (ከበሮ መቺ)፣ ታምራት ፈረንጅ (ትራምፔት ተጫዋችና ድምፃዊ)፣ ተክለ ዮሐንስ ዝቄ (ትራምፔት)፣ ተሾመ ምትኩ (ጋራ ሥር ነው ቤትሽ፣ ሞት አደላድሎን፣ ሃሳቤን የመሳሰሉት ዝነኛ ዜማዎቹ ይጠቀሳሉ) እና ቴዎድሮስ ምትኩ (ሳክሲፎኒስት) የመሳሰሉት ናቸው፡፡ እነዚህ የኰከበ ጽባሕ ፍሬዎች ከሶል ኤኰስ በፊትም ዙላ ባንድን መሥርተው ነበር፡፡ «ሶል ኤኰስ» ባንድን ወደ «አይቤክስ ባንድ» ከዚያም «ሮሃ ባንድ» ወዘተ. እየተባለ የስም ሽግግር በሚደረግበት ጊዜ ሁሉ እነዚያ ወጣቶች በንቃት ተሳታፊ ነበሩ፡፡
በዚያ ዘመን የነበሩት ብዙዎቹ የትምህርት ቤቶቹ የሙዚቃ ባንድ አባላት በሀገራችን የሙዚቃ ጥበብ ውስጥ ያበረከቱት አስተዋፅኦ ዛሬም ድረስ የደበዘዘ አይደለም፡፡ እንዲያውም ብዙ ታላላቅ የጥበቡ ሰዎችን አሁን ድረስ ለደረሱበት ደረጃ መሠረት የሆናቸውን መደላድል ጥቀሱ ቢባሉ ያለጥርጥር ምሥጋና የሚያቀርቡት ላሳደጋቸው የየትምህርት ቤቱ የሙዚቃ ባንድ እንደሆነ መገመት አይገድም፡፡
ይህ ታላቅ የጥበብ መክሊት በዛሬዎቹ ትምህርት ቤቶቻችን ውስጥ አለወይ? ርግጥ የዕውቀትና የጥበብ ሁሉ መፍለቂያው ትምህርት ቤት መሆኑ መስካሪ አያሻውም፡፡ ግን ግን በየትምህርት ቤቱ ለዛሬውም ሆነ ለነገው ሙዚቃችን መሠረት ሊሆን የሚችል ሥራ እየተሠራ ነው? ከመደበኛው ሥርዓተ ትምህርት ጐን ለጎን ለሙዚቃ ጥበብ እየተሠጠ ያለው ትኩረት ምን ያህል ነው? የትምህርት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታችን «የተቀበረውን ውጤታማ መክሊት» ቆፍሮ ለማውጣት ምን እየሠራ ይሆን? ዳግማዊ ምኒልክ፣ ኰከበ ጽባሕ፣ ወ/ሮ ስሂን … ትምህርት ቤቶችስ «ነበር» ታሪካቸውን ማደስ አይገባቸውምን? የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወድቋል ወይም ተነስቷል እያልን መከራከራችን ብቻ በራሱ በቂ ይሆናልን? ምን ያህሉን መክሊቶቻችንስ አርቀን በመቆፈር ያለማስተዋል ቋጥኝ ጭነንባቸው ቀበርናቸው ይሆን? እንወያይበት፣ እንምከርበት፡፡ ከንባቤ ጎን ለጎን ለዚህ ጽሑፍ በቂ ግብዓት በመስጠት የተባበሩኝን አርቲስት እሸቱ ጥሩነህ፣ ደራሲና ሃያሲ አስፋው ዳምጤና አቶ ተክለዮሐንስ ዝቄን ክብረት ይስጥልኝ በማለት በአንባቢያን ስም የማመሰግነው በታላቅ አክብሮት ነው፡፡ ሰላም፡፡

የአማራ ዴ/ኃ/ን ለሱዳን ተላልፎ በተሰጠው መሬት ዙሪያ “ዳሩ ካልተጠበቀ መሃሉ ዳር ይሆናል” የሚል መግለጫ አወጣ

$
0
0

Amara Democratic Force
ጋዜጣዊ መግለጫ 

“ዳሩ ካልተጠበቀ መሃሉ ዳር ይሆናል”!!

ከአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) የተሰጠ መግለጫ

ታህሣሥ 10 ቀን 2006 ዓ.ም.

በዓለም ላይ እስከአሁን የተከሰቱ መንግሥታት (ቅኝ ገዥዎችን ጨምሮ) ጨቋኝ (አምባገነን)፣ በዝበዥ፣ ዘራፊ (በሙስና የተዘፈቀ) … ወዘተ ሊሆኑ ይችላሉ። አሁን ኢትዮጵያን በመግዛት ላይ እንዳለው የትግሬ ዘረኛ ቡድን የሚገዛትን ሀገርና ሕዝብ የሚጠላና ሀገሩንም ለማጥፋት 24 ሰዓት የሚሠራ መንግሥት ግን እስከ አሁን በታሪክ አልታየም። ወደፊትም ከወያኔ በስተቀር የሚገዛትን ሀገር፣ ታሪኳንና ሕዝቧን የሚጠላና ሆን ብሎ ለማጥፋትም ቀን – ተሌት የሚጥር መንግሥት በምድር ላይ ይከሰታል ብለን አናምንም። ይህ የትግሬ ዘረኛ ቡድን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን መጥላቱን የሚያሳይ የድርጊቱን ሥንክሣር መዘርዘር ቢቻልም፣ በአሁኑ ሰዓት የተከሰቱ ሁለት ታላላቅ ብሔራዊ ጉዳዮችን ብቻ እንኳ ብናይ ዘረኛው ቡድን ምን ያህል የሚገዛትን ሀገርና ሕዝቧን አምርሮ እንደሚጠላ ፍንትው አድርገው ያሳያሉ፦

  1. በሣዑዲ አረቢያ የወገኖቻችን ደም  በግፍ ሲፈስስ፣ እህቶቻችን ያለርህራሄ በቡድን ሲደፈሩ፣ በ21ኛው ክ/ዘመን በሰው ልጅ ላይ የፈፀማል ተብሎ የማይታሰብ ኢሰብአዊ ግፍ ሲፈፀምባቸውና በአጠቃላይ በሀገሪቱ ላይ ብሔራዊ ውርደት ሲደርስ የትግሬው ዘረኛ ቡድን “የሣዑዲ አረቢያ መንግሥት በሀገሩ ላይ ይህንን ማድረግ መብቱ ነው” ነበር ያለው።
  2. በዚህ ሰቅጣጭ ሐዘን ውስጥ ተውጠንና በስቃይ ላይ ያሉ ወገኖቻችንን ለመርዳት ላይ ታች በምንልበት ጊዜ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ታጥቆ የተነሳው የትግሬው ዘረኛ ቡድን አባቶቻችን ደማቸውን በማፍሰስና አጥንታቸውን በመከስከስ ጠብቀው ያቆዩትን 1600 ኪ/ሜ ርዝመትና ከ20-60 ኪ/ሜ ወደ ኢትዮጵያ ጥልቆ የሚገባውን ከሱዳን የሚያዋስነውን ድንበራችንን በሕገወጥነት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ፈርሞ ለሱዳን አስረከበ። ምንም እንኳን በሚስጥር ሊይዘው ቢሞክርም የድንምበር ማካለሉ ከጥር ወር 2006 እስከ መስከረም 2007 ችካል በመቸከል እንደሚጠናቀቅ ታውቋል።

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) ይህንን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ የሚደረግ ሕገወጥ የድንበር ክለላ አጥብቆ መቃወምና ማውገዝ ብቻ ሳይሆን እንዳባቶቹ ደሙን አፍስሶና አጥንቱን ከስክሶ ታሪካዊ ድንበሩን ለማስከበር ቆርጦ ተነስቷል። ባንዳ የባንዳ ልጆች ከአባቶቻቸው የወረሱትን ሀገር የማጥፋትና የመሸጥ ውርስ ተግባራዊ ሲያደርጉ እኛ የአርበኛ ልጆች ነን የመንል ይህንን ደባ ዝም ብለን ብንመለከት ድንበር ላይ የተከሰከሰው የአባቶቻችን አጥንት እሾህ ሆኖ ይዎጋናል። በመሆኑም በአካባቢው ያላችሁ ታጋይ ኃይሎችና የገፈቱ ቀማሽ የሆንከው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በርስቱና በሚስቱ ያልሞተ ወንድ ልጅ ወንድ አይደለምና ወንድ ልጅ ነኝ ያልክ ሁሉ ተባበረን፣ ከዚህ በላይ የሞት ሞት የለምና።

አዴኃን ይህንን ድርጊት አምርሮ የሚቃወመው እንዲያው በጭፍኑ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር ሕጋዊ የሆነ ድንበር አይኑራት ብሎ አይደለም። የድንበር ስምምነቱ ኢትዮጵያን ጎድቶ ሱዳንን የሚጠቅም፣ ከ110 ዓመታት በፊት የፈረሰና ሕጋዊ ያልሆነ ውልን መሠረት ያደረገ፣ በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ጥናት ያደረጉ ኢትዮጵያውያንን ጥናትና ውትወታ ግንዛቤ ውስጥ ያላስገባና በአጠቃላይ ከኢትዮጵያ  ሕዝብ ጀርባ በደባና በሕገወጥነት የተፈረመ ውል በመሆኑ እንጅ።

በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ጥናት ያደረገው የኢትዮጵያ የድንበር ኮሚቴና ከዚያ በፊትም ጥናት ያደረጉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምሑራን እንደሚሉን ከሆነ ይህ ዛሬ የትግሬው ዘረኛ ቡድን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ለተፈራረመው ውል ዋቢ የሚያደርገው ውል በዳግማዊ አፄ ምኒልክና በጊዜው የሱዳን ቅኝ ገዥ በነበረችው እንግሊዝ መካከል የተፈረመው እ.አ.አ 1902 ነበር። አፄ ምኒልክ ይህንን ውል የፈረሙት በኃይል ተገድደውና በይዞታቸው ሥር የነበሩ ብዙ መሬቶችን ለቀው ነበር። በዓመቱ በ1903 የእንግሊዙ የጦር መኮንን ሻለቃ ጉዊን ድንበሩን ከስምምነቱ ውጭ ብቻውን ሄዶ ከመከለሉም በላይ አፄ ምኒልክ ተገድደውም ቢሆን የፈረሙትን ካርታ አዛብቶ ኢትዮጵያን እየጎዳ ችካል ቸከለ። ይህንንም ሻለቃ ጉዊን ከተሰጠው ሥልጣን በላይ ሄዶ መሥመሩን በማዛባት ከኢትዮጵያ መሬት እንደወሰደ በራሱ ሪፖረት ላይ በግልፅ ሳይደብቅ ጽፏል። እንግሊዞችም በ1902 የተፈረመበትን ካርታ ጥለው በችካሉ መሠረት በ1903 አዲስ ካርታ በመሥራት እነርሱ ከፈረሙበት በኋላ አፄ ምኒልክን ለማስፈረም ቢሞክሩም ከስምምነት ውጭ ለተቸከለው የጉዊን ክለላ ዕውቅና በመንፈግ ሳይፈርሙበት ቀርተዋል። የትግሬው ዘረኛ ቡድን አፄ ምኒልክ፣ አፄ ኃይለሥላሴና ደርግ የጉዊንን መሥመር ተቀብለዋል እያለ የሚያላዝነው ይህንን የመሰለውን ሐቅ በመካድ ነው። ይህንንም ዓይን ያወጣ የወያኔን ቅጥፈት አዴኃን ብቻ ሳይሆን ሰኞ 19 ኖቬምበር 2007 (እ.አ.አ.) ሱዳን ትሪቢዩን የተባለ ጋዜጣም “ድንበሩን አስመልክቶ የሱዳን መንግሥት ከቀደምት የኢትዮጵያ መንግሥታት ጋር የነበረው ግንኙነት ቀና አልነበረም። በድንበሩ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር የመጀመሪያው ፈቃደኛ መንግሥት ገዥው የኢሕአዴግ መንግሥት ብቻ ነው” በማለት መሥክሮበታል።

ጥሪ፦     

ውድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! የፖለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ ማህበራትም ጭምር፣ ይህ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ በሀገር ከሃዲው የትግሬ ዘረኛ ቡድ ከጎንደር፣ ከጎጃም፣ ከወለጋና ከኢሊባቡር ክፍለ ሀገሮች ተቆርሶ ለሱዳን የሚሰጠው ለም መሬት የክፍለ ሀገራት ተወላጆቹ መሬት ብቻ አይደለም፤ የአንተም የኢትዮጵያዊው መሬት እንጅ። በመሆኑም አዴኃን ይህንን በባንዳ ልጆች የተጋረጥብንን ኢትዮጵያን የማጥፋት ታላቅ አደጋ ለመቀልበስ ስንል ያሉንን ጥቃቅን ልዩነቶች ወደጎን በመተው፣ ከምንጊዜውም በላይ እጅ ለእጅ ተያይዘንና ያለንን አቅም ሁሉ አስተባብረን በመነሳት የዜግነት ግዴታችን እንድንወጣ አስቸኳይ ጥሪውን ያስተላልፋል። “ዳሩ ክልተጠበቀ፣ መሀሉ ዳር ይሆናል” እንደሚባለው የትግሬውን ዘረኛ ቡድን በተባበረ ክንድ ዛሬውኑ ካላስወገድነው በስተቀር እናት ሀገራችን ኢትዮጵያን የማፈራረስ ዕኩይ ተልዕኮው የድንበር መሬቶችን እየቆረሰ ለጎረቤት ሀገራት በመስጠት ብቻ ያቆማል ብሎ ማሰብ ፍፁም የዋህነት ነው።

ለመከላከያ ሠራዊት፣ የፖሊስ ኃይልና የኢሕአዴግ ደጋፊዎች፣ እናንተ የምትደግፉት ሀገር አጥፊው የትግሬ ዘረኛ ቡድን አባቶቻችን ደረታቸውን ለጦር፣ እግራቸውን ለጠጠር ሰጥተው በደማቸው ያቆዩአትን ይህችን ጥንታዊትና ታሪካዊት ሀገራችንን እያጠፋት እንደሆነ ለእናነተ የተሠወረ አይደለም። ይህንን ሀገር የማጥፋት ወንጀል የሚፈፅመው ደግሞ እናንተን በመሣሪያነት በመጠቀም ስለሆነ ይህንን ተገንዝባችሁ አሁኑኑ ከሕዝባችንና አደጋውን ለመቀልበስ ከሚታገሉ ኃይሎች ጎን በመቆም ሀገራችሁን እንድትታደጉ ስናሳስብ፣ ጥሪያችን ችላ በማለት ለሀገር አጥፊው ቡድን ተባባሪነታችሁን ከቀጠላችሁበት ግን ታሪክና ሕዝብ ይቅር እንደማይላችሁ በጥብቅ ልናስጠነቅቃችሁ እንወዳለን።

ለብአዴን አባላት፦ “እሣት አመድ ይወልዳል” እንደተባለው ካልሆነ በስተቀር፣ አባቶቻችሁ ኢትዮጵያን ከሚያጠፋ ጠላት ጋር ተባብረው እናት ሀገራቸውን አላጠፉም፤ ይልቁንም ደማቸውን አፍስሰውና አጥንታቸውን ከስክሰው የታፈረችና አንድነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለእናንተ አስረከቧችሁ እንጅ። እናንተ ግን የጀግኖች አባቶቻችሁ የባሕሪ ልጆች መሆን አቅቷችሁና አደራቸውን በልታችሁ ኢትዮጵያን ለማፈራረስና አማራን ለማጥፋት ቆርጦ ለተነሳው የትግሬ ዘረኛ ቡድን አሽከር ሆናችሁ እናት ሀገራችሁንና ወገናችሁን እያጠፋችሁ ነው። “ለእንጀራየ፣ ለልጆቼና ለቤተሰቦቼ ስል ወይም ተገድጀ ነው ይህንን የማደርገው” የሚለው ውሃ የማይቋጥር ምክንያት እንደማያዋጣችሁ አውቃችሁ የጋራ ሀገራችንንና ወገናችንን ለመታደግ አብራችሁት እንደትቆሙ አዴኃን ከልብ የመነጨ የሀገር አድን ጥሪ ያቀርብላችኋል።

ወንድም ለሆነው የሱዳን ሕዝብ፦ የኢትዮጵያና የሱዳን ሕዝብ ለብዙ ሺህ ዘመናት ከአንድ ወንዝ ከተቀዳ ውሃ እየጠጣ፣ በመከባበር ላይ በተመሠረተና በመልካም ጉርብትና አንዱ ለሌላው የችግር ጊዜ ደራሽ ሆኖ የኖረ ወንድማማች ሕዝብ ነው። ነገር ግን ዛሬ የትግሬው ዘረኛ ቡድን በሀገር ውስጥ የሚገኙ ነገዶችን እርስ በእርሳቸው ከማናከስ አልፎ የኢትዮጵያን ሕዝብ በተለይም የአማራውን ነገድ ወንድም ከሆነው የሱዳን ሕዝብም ለማናከስ ቆርጦ የተነሳ በመሆኑ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ዕውቅና ውጭ የተፈረመን የድንበር ስምምነት እንዳይቀበል በጥብቅ እናሳስባለን።

በመጨረሻም የዓለም ምንግሥታትና ዓለም – አቀፍ ሠላም ወዳድ ሕብረተሰብም የወያኔ ዘረኛ ቡድን ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ሕዝብ ፈፅሞ እንደማይወክልና አሁን ከሱዳን መንግሥት ጋር በድብቅ የተፈራረመውንም የድንበር ስምምነት ንቅናቄያችን አዴኃን እና የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደማያውቁት ተገንዝበው ስምምነቱ አሁንም ይሁን ወደፊት በሁለቱ ሀገራት ሕዝብ መካከል የሚፈጠረውን ቀውስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ለስምምነቱ ዕውቅና እንዳይሰጡና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚፈፀመውን ይህንን ሤራ እንዲቃወሙ አዴኃን ጥሪውን ያስተላልፋል።

በደም የተረከብናትን ሀገር በደም እንጠብቃታለን!!

 

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ


የኢህአዴግ አዲሱ አሰላለፍ ፪ –ከተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)

$
0
0

samora and azeb

በድህረ-መለስ ኢትዮጵያ የፖለቲካው ሥልጣን በስርዓቱ ልሂቃን መካከል ከሚደረገው የኃይል መተናነቅ አንጻር፣ ዛሬም ከመፈራረቅ ጣጣው የተላቀቀ የማይመስልባቸው ምልክቶች መታየታቸው እንደቀጠለ ነው፡፡ ከአራት ወር በፊት በዚህ መፅሄት ላይ ‹‹አዲሱ የኢህአዴግ አሰላለፍ›› በሚል ባቀረብኩት ፅሁፍ በገዥው ፓርቲ ውስጥ ተፈጥሮ ከነበረው ክፍፍል የትኛው ቡድን የበለጠ ጉልበት አግኝቶ በአሸናፊነት መውጣት እንደቻለ ከገለፅኩ በኋላ ፅሁፉን የቋጨሁት እንዲህ በማለት ነበር፡- ‹‹የፓርቲው የታሪክ ድርሳን እንደሚነግረን ‹ይሆናሉ› የተባሉት ተቀልብሰው፣ ባልተጠበቁ ሁነቶች (የኃይል መገለባበጥ ተከስቶ) ፖለቲካው የሚመራበት አጋጣሚ ሊፈጠር የሚችልበት ዕድል ሊኖር እንደሚችልም መዘንጋት አያስፈልግም፡፡››

እነሆ በዚህ ፅሁፍ ደግሞ በቅርቡ በተጨባጭ የታዩትን አዳዲስ ኩነቶች እና ይህንኑ ተከትለው ሊመጡ ይችላሉ ብዬ የምገምታቸውን ‹የቢሆን ዕድሎች› (Scenarios) ለማየት እሞክራለሁ፡፡
ሰላም የራቀው-ኢህአዴግ
በግንባሩ አባል ድርጅቶች መካከል ዛሬም ድረስ ሙሉ በሙሉ የተረጋጋ ፖለቲካ አልሰፈነም፤ የዚህ ዋነኛ ምክንያቱ ደግሞ፣ ቁልፍ የሥልጣን ቦታዎችን ጠቅልሎ ይዞ በነበረው በቀድሞ ሊቀ-መንበሩ ህልፈት ሳቢያ የተፈጠረው የአመራር ክፍተት እና እርሱን ሊተካ የሚችል መሪ ማግኘት ባለመቻሉ ይመስለኛል፡፡ እንዲህ አይነት አጋጣሚዎችም በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ከሕግ ይልቅ የጠመንጃ ኃይልና የግለሰብ አምባገነናዊነት በገነነበት ሀገር ‹የማይገመቱ ክስተቶች› (Unpredictable Event) ማምጣታቸው የሚጠበቅ ነው፡፡

የሆነው ሆኖ በዚህ አጀንዳ ለመመልከት የምሞክረው ጉዳይ፣ በአሁኑ ጊዜ ሀገር እየመራ ያለው ኃይል ለሁለት የተከፈለ ቢሆንም፣ በአንፃራዊነት በጥምር የሚሰራ መሆኑን በማስረገጥ ነው፡፡ የእነዚህ ሁለት ቡድኖች የጉልበት ምንጭም የታጠቀውን ኃይል በመቆጣጠር እና የፖለቲካውን ሥልጣን በመያዝ ላይ የተመሰረተ ነው፤ ይኸውም ሠራዊቱ እና የደህንነት መስሪያ ቤቱ ሙሉ በሙሉ በህወሓት ሰዎች ሲንቀሳቀሱ፣ ፖለቲካውን ደግሞ የብአዴን መሪዎች፣ ከተወሰኑ የኦህዴድና ደህአዴን የአመራር አባላት ጋር ተባብረው መያዛቸውን የሚያሳዩ ምልክቶች መኖራቸው ነው፡፡

የህወሓት ኃይል

ህወሓት የቀድሞው ፍፁማዊ የበላይነቱን ለመመለስ ዋና ችግር የሆነበት በውስጡ ለተፈጠረው መከፋፈል እስካሁን መፍትሄው ተለይቶ አለመታወቁ ነው፤ ከዚህ ቀደም በዚሁ መፅሄት፣ አንዱ ኃይል የተሻለ ጉልበት በማግኘቱ ሌላኛውን (እነአዜብ መስፍንን ጨምሮ አባይ ወልዱና ቴዎድሮስ ሀጎስን የመሳሰሉ ከፍተኛ ካድሬዎች የተሰባሰቡበትን) በመብለጥ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን እንቅስቃሴያቸውን መገደቡ ተሳክቶለት እንደነበረ ማስነበቤ ይታወሳል፡፡ ይህ ክፍፍል ምንም እንኳ እንደ 1993ቱ ከፓርቲ እስከ ማስወጣት የሚደርስ አለመሆኑ ቢታወቅም፣ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል እና ጌታቸው አሰፋ የተሰለፉበት ቡድን ተፅእኖ ፈጣሪ ሆኖ መውጣት ችሏል፤ ይህም ሆኖ ውስጥ ውስጡን የሚገመደው ተንኮልም ሆነ ሽኩቻ ገና መቋጫ አለማግኘቱ ግልፅ ነው፡፡
በዚህ ፅሁፍ ጠመንጃ የታጠቀውን ክፍል ‹የህወሓት ኃይል› እያልኩ የምገልፀበት ዓብይ ምክንያት፣ በጄነራል ሳሞራ የኑስ ኤታ ማዦር ሹምነት የሚመራው የመከላከያ ሠራዊት እና በማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ጌታቸው አሰፋ ስር ያለው የደህንነት ኃይል ለሚደግፉት ቡድን መጠናከር እያበረከቱት ያለውን አስተዋፅኦ ከግምት በመክተት ነው፡፡ ሁለቱም ሰዎች ለመለስ ፍፁም ታማኝ የነበሩ ቢሆንም፣ ከህልፈቱ በኋላ እንደእርሱ ተጭኖ ሊቆጣጠራቸው የሚችል ጉልበታም ህወሓትን ጨምሮ በሁሉም የግንባሩ አባል ፓርቲ ውስጥ አለመኖሩ፣ በፖለቲካው ‹ቼዝ› የ‹ዘመነ መሳፍንቱ›ን ሚካኤል ስሁል አይነት ሚና እንዲጫወቱ አስችሏቸዋል፤ ሁለቱም ከስራቸው የነበሩትንና ‹ስልጣን ሊጋፉ ይችላሉ› ብለው የጠረጠሯቸውን ባልደረቦቻቸውን አስቀድሞ ገለል ማድረጉ ከሞላ ጎደል የተሳካላቸው ይመስለኛል፡፡
በተለይም ጌታቸው አሰፋ ከራሱ ወንበር አልፎ ከእነአዜብ መስፍንና አባይ ወልዱ ጋር በመተባበር አንድ ቀን በጠቅላላው የመንግስት የሥልጣን እርከን ላይ ‹ናቡቴ ሊሆን ይችላል› የሚል ስጋት ያሳደረበትን እና ‹መለስ ዜናዊ ሞት ባይቀድመው በእርሱ ቦታ ሊተካው ነበር› እየተባለ የሚነገርለትን የመረጃ ኃላፊ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል በሙስና የሚወነጀልበትን መንገድ አመቻችቶ ለእስር ባይዳርገው ኖሮ ‹‹ለቁርስ ያሰቡንን…›› አይነት ታሪክ ራሱን መድገሙ አይቀሬ ነበር ብዬ አስባለሁ፡፡
ጄነራል ሳሞራ የኑስ በበኩሉ ተቀናቃኙ አድርጎ ይመለከታቸው የነበረው ሶስቱ ከፍተኛ መኮንኖች እንደ ወልደስላሴ ‹ፍንቀላ መሳይ ነገር ሊሞክሩ ይችላሉ› ተብለው አይደለም፡፡ የእነርሱ የመጀመሪያው ችግር ከወታደራዊ ዲሲፕሊን በማፈንገጥ አለቃቸውን አለማክበራቸው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ሳሞራ ‹በየትኛውም ምክንያት ከኃላፊነቴ ብነሳ የቆየ ፋይል አገላብጠው አደጋ ላይ ሊጥሉኝ ይችላሉ› በሚል ስለሚጠረጥራቸው ነው፡፡ እነዚህ መኮንኖች የሰሜን ዕዝ አዛዥ ሌፍተናንት ጄነራል ሰዓረ መኮንን፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ መልካም ግንኙነታቸው እንደቀድሞው እንዳልሆነ የሚነገረው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌፍተናንት ጄነራል አበባው ታደሰ እና የአየር ኃይሉ አዛዥ ሜጀር ጄነራል ሞላ ኃይለማርያም ናቸው፡፡ እናም ሰዓረ እና አበባው በቀጥታ ሠራዊት ከሚያዙበት ቦታ ተነስተው በመከላከያ ሚኒስትር ውስጥ በቢሮ ስራ ላይ ሲመደቡ፣ ሞላም ከነበረበት ኃላፊነት አኳያ ብዙም ይመጥነዋል የማይባል የቢሮ ስራ ተሰጥቶታል፤ በእርሱም ቦታ ሜጀር ጄነራል አደም መሀመድ ተተክቷል፡፡ የሳሞራ እና የሞላ ልዩነት በመለስ ዘመንም በአደባባይ የሚታወቅ እንደነበረ ሰምቻለሁ፡፡
Samora (2)
ለጉዳዩ ቅርብ ከሆነ የመረጃ ምንጬ እንዳረጋገጥኩት የአስተዳደር ዘይቤውን በማኪያቬሊያዊ አስተሳሰብ (ከፋፍለህ ግዛ) የሚያሳልጠው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ ለሞላ ትዕዛዝ የሚሰጠውም ሆነ ማንኛውንም ጉዳይ በተመለከተ የሚያነጋግረው የዕዝ ተዋረዱን ጠብቆ በኤታ ማዦሩ በኩል ሳይሆን፣ በቀጥታ በመገናኘት መሆኑ፣ አየር ኃይሉን ከመከላከያ ሚኒስቴር የተገነጠለ አስመስሎት ነበር፤ ይህ ሁኔታም በሁለቱ መኮንኖች መካከል ያለው ግንኙነት የሥልጣን ተዋረድን የጠበቀ እንዳይሆን በማሰናከሉ በጄነራሉ ላይ ደፍሮ የማይናገረው ቅሬታ ሊያሳድርበት ችሏል፤ ከመለስ ህልፈት በኋላም ሳሞራ ሂደቱን ለማስተካከል መሞከሩ፣ በየግምገማው ላይ እስከ መዘላለፍ አድርሷቸው ነበር (በነገራችን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ወደ ሥልጣን ከመጣ በኋላ እንደ ጦር ኃይሎች አዛዥነቱ፣ ከጄነራሎቹ ጋር መደበኛ /Official/ በሆነ መንገድ ትውውቅ አላደረገም፤ እነዚህ ሶስት ጄነራሎችም ለዚህ አይነቱ የአሰራር መፋለስ ጥፋተኛ የሚያደርጉት አለቃቸውን ሳሞራ የኑስን ነው፤ ከምንጮቼ እንደሰማሁት ከሆነም ከወራት በፊት ኃይለማርያም ደሳለኝ በተገኘበት ‹ጎልፍ ክለብ› በሚባለው የጄነራሎቹ መዝናኛ በተዘጋጀ ፕሮግራም ማጠናቀቂያ ላይ ሳሞራ አንድ ጠረጴዛ ከበው ወደ
ተቀመጡት እነዚህ ጄነራሎች ጋ ሄዶ ‹ኑ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ላስተዋውቃችሁ› ማለቱን እና እነርሱም በጥያቄው ተበሳጭተው ቢሮ ያላቸው መሆኑን እና ክብራቸውን በሚመጥን መልኩ መተዋወቅ እንደነበረባቸው በኃይለ ቃል መመለሳቸውን ነው)

የሳሞራ የኑስ እና ሰዓረ መኮንን መነቋቆር ከትግሉ ዘመን ጀምሮ የመጣ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ሳሞራ ከማንም በላይ የሚፎካከረውም ሆነ መበለጥ የማይፈልገው በሟቹ ጄነራል ኃየሎም አርአያ እንደ ነበር የቀድሞ ጓዶቻቸው ያስታውሳሉ፤ ይህ ሁኔታ ዛሬም ድረስ በስራ ላይ ያሉ መኮንኖችን ‹የሳሞራ› ወይም ‹የኃየሎም ተከታይ› በማለት መከፋፈሉ በጓዶቻቸው እና በፓርቲው መሪዎች አካባቢ የሚታወቅ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ለማዕረግ እድገት የተለየ የድጋፍ አስተያየት የሚያገኙት በዛን ዘመን ‹የሳሞራ ተከታይ› የሚባሉት እየተመረጡ እንደነበረ በወሬ ደረጃ ይናፈሳል (በነገራችን ላይ ጄነራል ሳሞራ ከጤንነት ጋር በተያያዘ በአጭር ጊዜ ውስጥ በጡረታ ይሰናበታል በተባለበት ጉዳይ ላይ እያንገራገረ እንደሆነ ከመከላከያ አካባቢ የሚወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ፤ እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው ደግሞ ‹ለእኔ በጎ አመለካከት የላቸውም› በሚል የሚጠራጠራቸው ጄነራሎች በሥራ ላይ እያሉ የእሱ ጡረታ መውጣት ከመስሪያ ቤቱ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ያደሩ የሙስና ካርዶች የሚመዘዙበትን ዕድል ያሰፋዋል የሚል ነው፤ በተለይም በግዙፍ የቢዝነስ ሥራዎች ላይ በታላቅ ተፎካካሪነት እየተሳተፈ የሚገኘው ‹መቴክ› ምንም እንኳ ማረጋገጫዎች ባይቀርቡበትም በመከላከያ ሥር ከነበረበት ዘመን እስከ 2002 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ ከግዥዎች ጋር ተያይዘው የሚነሱ በርካታ የሙስና ሁኔታዎች በመኖራቸው ነው፡፡
መቴክ ካለፉት አራት ዓመታት ጀምሮ በአዋጅ የልማት ድርጅት እንዲሆን ቢደረግም፣ ዛሬም ዳይሬክተሩ የሠራዊቱ አባል ብርጋዴር ጄነራል ክንፈ ሲሆን፣ መከላከያ ደሞዝ የሚከፍላቸው ጥቂት የማይባሉ ሠራተኞችንም እንዳቀፈ ይታወቃል፡፡ እናም ሳሞራ ሃሳቡ ከተሳካለት ለጥቂት ተጨማሪ ዓመታት በሥልጣኑ ላይ ሲቀጥል፣ አሊያም ‹የወንድ በር› ለማግኘት በትግሉ ዘመን የእርሱ ሰልጣኝ እንደነበረ የሚነገርለትን እና በቅርቡ ብቸኛው ከሜጀር ወደ ሌፍተናት ጄነራል ማዕረግ ያደገው ዮሀንስ ገ/መስቀል እንዲተካው መንገድ ጠረጋውን ማመቻቸቱ ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራበት ጉዳይ ይመስለኛል)
samora
ይህም ሆኖ የተኮረኮርን ያህል የምንስቀው ጄነራል ሳሞራ የኑስ በቅርቡ ለታተመው ‹‹ህብረ ብሔር›› መፅሄት ሙስና ለሠራዊቱ አደገኛ መሆኑን እንዲህ በማለት መግለፁን ስናነብ ነው፡-
‹‹ሙስና ሠራዊቱን ሊያበላሸው ይችላል፡፡ ሙስና ፀረ-ልማት ነው፤ ሠራዊቱን ሊበትነው እና ሕዝባዊ ባህሪውን እንዲያጠፋ ሊያደርገው ይችላል፤ አንድ ሠራዊት ሠራዊት ነው የሚባለው እንደ ወታደር እንደ አንድ አካል ሲያስብ እንጂ ለግሉ ሲያስብ አይደለም፡፡ …በአጠቃላይ (ሠራዊቱ) በዚህ ነው የሚፈርሰው፡፡››
መቼም ጄነራሉ ይህንን የተናገረው እራሱን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ መኮንኖች እንደ እንግሊዝ ንጉሳውያን ቤተሰቦች በተንጣለለ ቪላ ቤት ውስጥ፣ የተቀማጠለ ኑሮ መኖራቸውን ረስቶት አይመስለኝም፤ ‹ይህ የተንዛዛ ወጪያቸውም የሚሸፈነው ከደሞዛቸው በሚያገኙት ገቢ ነው› ብሎ ቧልት መሳይ ክርክር ሊያመጣ አይችልም፡፡ ይሁንና እታች ያለው ጭቁን የኢትዮጵያ ሠራዊት ምንም እንኳ በአለቆቹ ‹ቴክሳስ›ነት ላይ ለመቆጣት ባይደፍርም፣ እንደማንኛውም ዜጋ ለኑሮ ውድነትና አስከፊ ድህነት የተጋለጠ መሆኑን መካድ አይቻልም፡፡
የሆነው ሆኖ ተሰሚነታቸው እየተቀዛቀዘ የመጣው አቦይ ስብሃት ነጋ ከወራት በፊት ለ‹‹ውራይና›› መፅሔት ‹‹ህወሓት ትንሳኤ ያስፈልገዋል›› በማለት የሰጡትን ምክር ተከትሎ፣ ጄነራል ሳሞራ እና አቶ ጌታቸው አሰፋ፣ ከድርጅቱ ምክትል ሊቀ-መንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ጋር በመተባበር ህወሓትን ለማጠናከር እና በፖለቲካ ውስጥ የነበረውን የአንበሳውን ድርሻ ለማስከበር (ጉዳዩን ከለጠጥነው ደግሞ ‹ለማስመለስ›) እየሰሩ እንደሆነ ይነገራል (በነገራችን ላይ የሳሞራና ጌታቸው ተፅእኖ መጨመሩን ለመረዳት፣ መከላከያ ‹አገራዊ ጥቅምንና ደህንነትን ለመከላከል› በሚል ‹እጅግ ጥብቅ ሚስጢር ብሎ የሰየማቸውን የሰው ኃይል ፕሮፋይል፣ የሒሳብ መዝገቦችና ሰነዶች እና የክፍያ ማስረጃዎች ለማንም አካል እንዳይገለፅ› የሚያስችለውን ስልጣን፣ ደህንነቱ ደግሞ በስራ ላይ የሚፈፅማቸው ማንኛውም ጉዳዮች ወደፊት በህግ እንዳይጠይቅ እስከ መከላከል የሚደርሰውን አዲስ የተዘጋጁትን አዋጆች ማንበቡ በቂ ነው፡፡ በርግጥ እነዚህ ባለሥልጣናት እንዲህ ባለ ተመሳሳይ መንገድ እንዲጓዙ ያስተሳሰራቸው አንዱ ጉዳይ ‹ህወሓት ተዳከመ፣ ተሸነፈ፣ አበቃለት…› የሚለው የካድሬውና ደጋፊው ቁጭት እንጂ ወትሮም መልካም ግንኙነት ኖሯቸው አይመስለኝም)

ለማንኛውም በጥቅሉ ሲታይ የህወሓት ትልቁ ችግር ተብሎ በአመራር አባላቱ የሚጠቀሰው ‹በዚህ ወቅት ወደፊት መምጣት የሚችሉ ጠንካራ ቴክኖክራቶችን አለማፍራቱ፣ ሁለንተናዊ ድጋፍ የሚያደርግለትን የታጠቀውን ኃይል ተጠቅሞ የፖለቲካ ልዩነቱን ጨፍልቆ በአሸናፊነት ይዞት መውጣት የሚችል መሪ እንዳይኖረው አደረገ› የሚል ነው፡፡ በርካታ የላይኛ እና የታችኛው ካድሬዎችም ‹ለእንዲህ አይነቱ ክፉ ጊዜ ድርጅቱ የሚያስፈልገው፣ በትግሉ ዘመን ልምድ ያካበተ ታጋይ ብቻ ነው› የሚል አቋም እንዳላቸው ይነገራል፡፡ ስርዓቱ ከሚያራምደው ርዕዮተ-ዓለም ጋር ጠንካራ ትውውቅ ያሌለውን እና የትግሉን ዘመን በአሜሪካን ሀገር በማሳለፉ ‹የምዕራባውያን ድጋፍ አለው› ለሚባለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የሚሰጡት ዝቅተኛ አመለካከት መግፍኤም ይኸው ይመስለኛል፡፡
ለነገሩ እርሱም ቢሆን በጠንካራ ድርጅታዊ ዲሲፕሊን ካለመታነፁ እና መሰል ጉዳዮች ጋር በሚያያዙ ምክንያቶች ለትንፋሽ ጊዜ የማይሰጠውን የድርጅት ሊቀ-መንበርነትንም ሆነ የጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ የሚወራውን ያህል ይፈልገዋል ብሎ መደምደሙ አስቸጋሪ ነው ብዬ አስባለሁ፤ ከዚህ ይልቅ በተፈጥሮ ከታደለው የተግባቢነት ባህሪው አኳያ እንደ ሕዝብ ግንኙነት የመሳሰለ ብዙም የማያጨናንቅ ሥራን ይመርጣል፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ከሰለጠነበት ሙያ ጋር የቀጥታ ተያያዥነት ያለውን የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በሚመራበት ዘመን፣ ከውጭ ሀገር በርካታ የተቋረጡ ፈንዶችን እንደገና ለማስለቀቅ መቻሉ እንደ ታላቅ ስኬት የሚወራለት፤ አልፎ ተርፎም ‹ወባን ከኢትዮጵያ ምድር ለማጥፋት ብርቱ ትግል አደረገ› ተብሎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሳይቀር እስከ መሸለም የደረሰው እዚህ መስሪያ ቤት እያለ እንደሆነም ይታወቃል፡፡

ትንቅንቅ

ትንቅንቅ


በሌላ በኩል ደግሞ በፓርቲውም ሆነ በመንግስት አስተዳደር ከህወሓት ሰዎች ትልቁን ስልጣን የያዘው ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከምዕራባውያን ጋር የቆየ ቀረቤታ እንዳለው ሰምቻለሁ፤ እንደሚታወሰው ደብረፅዮን ከክፍፍሉ በፊት (የደህንነት መስሪያ ቤቱ እንዲህ እንደ ዛሬው እጅግ ዘመናዊ በሆነው የቻይና ቴክኖሎጂ ሳይጥለቀለቅ) ከነበረው ከፍተኛ የሥልጣን ቦታ ላይ ተነስቶ፣ ቁልቁል ወርዶ በሁመራ በአንድ ዞን እንዲሰራ የተመደበው (ሁላችንም ስንገምት እንደነበረው) የአንጃው አባል ወይም ደጋፊ ሆኖ አይደለም፤ ይልቁንም የእነስዬ-ተወልደ ቡድን በመባል የሚታወቀው (‹አፈንጋጩ› ኃይል) ደብረፅዮንን በሲ.አይ.ኤ እና ሞሳድ ወኪልነት የመክሰሱ ጉዳይ የድርጅቱን በርካታ አባላት ቀልብ በመሳቡ፣ መለስ ይህንን ተከትሎ ከሚመጣበት አደጋ ራሱን ለመከላከል የወሰደው እርምጃ በመሆኑ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት እስከ 1998 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ በሁመራና ራያ አካባቢዎች በዞን ደረጃ ለማገልገል ተገዷል፡፡ እናም እርሱን የምዕራቡ ዓለም ፊት-አውራሪ አሜሪካና ሸሪኮቿ ወዳጅ ነው የሚያስብለው በቀድሞ መስሪያ ቤቱ በኩል በነበረው ግንኙነት ይመስለኛል።

የፖለቲካውን መዘውር የጨበጠው ኃይል

የዚህ ቡድን አምበል እንደ ድርጅት ብአዴን ቢሆንም፣ በቋሚ ተሰላፊነት ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ አባዱላ ገመዳ፣ ሙክታር ከድር እና ሬድዋን ሁሴን እንደሚገኙበት ይነገራል፤ ለብአዴን ‹በተሻለ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ላይ ለመገኘቱ መደላድል ፈጥሮለታል› የሚለውን ሙግት ምክንያታዊ የሚያደርገው ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊሲና ጥናት ምርምር አማካሪ በረከት ስምዖን፣ የኢህአዴግን የካድሬ ማሰልጠኛ ማዕከል በዳይሬክተርነት የሚመራው አዲሱ ለገሰ፣ ደርቦ ይዞት የነበረውን የትምህርት ሚኒስትርነት ለሽፈራው ደሳለኝ በመልቀቅ፣ በአሁኑ ወቅት ሙሉ የስራ ጊዜውን በግንባሩ ፅ/ቤት የሚያውለው ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እና የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባኤው ካሳ ተክለብርሃን የያዙት ሥልጣን ያለውን የፖለቲካ አቅም መመዘኑ ይመስለኛል፡፡ በመከላከያ ሠራዊቱ ውስጥም ከሳሞራ አንድ እርከን ዝቅ ባለ ሥልጣን ከሌሎች ሁለት ጄነራሎች ጋር የሚገኘው አበባው ታደሰ እንደ ቀድሞው በዕዝ አዛዥነቱ (በቀጥታ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ወታደሮችን ማንቀሳቀስ የሚችልበት) ላይ ቢሆን ኖሮ ጥንካሬውን የተሟላ ማድረጉ አይቀሬ እንደነበረ መገመት ይቻላል፡፡

ከዚህ ሌላ ለእነበረከት ቡድን ተጨማሪ የፖለቲካ ጉልበት እየሆናቸው ያለው የኃይለማርያም ደሳለኝ ቢሮ እና በአባዱላ ገመዳ አፈ-ጉባኤነት የሚመራው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ነው፡፡ አባዱላ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ለማቅረብም ሆነ ለመታዘዝ ፍቃደኛ ያልሆኑ አንዳንድ ባለስልጣናት፣ በውስጥ መስመር በሚተላለፍለት ‹ጥቅሻ› በምክር ቤቱ በኩል የሚመለከተው የቋሚ ኮሚቴ አባላት አስጠርቶ የተሰጠውን ኃላፊነት የሚገመግምበት ስልት እየተገበረ ነው፡፡ በአናቱም ምን ጊዜም የሳምንቱን የሥራ መጨረሻ ቀን አርብን ጠብቆ የሚሰበሰበው የሚኒስትሮች ም/ቤትን ከሞላ ጎደል ይህ ቡድን እየጠቀመበት ይመስለኛል፡፡ በርግጥ ሚኒስትሮቹ በሚገናኙበት አብዛኛውን ሰዓት ሳይግባቡ (በጭቅጭቅ) ማሳለፋቸው ይነገራል፤ የዚህ ምክንያቱ ደግሞ በአቶ መለስ ዘመን ም/ቤቱ የሚሰበሰበው የተለያዩ አጀንዳዎችን ለማቅረብ እና በቀረበው አጀንዳ ላይ ለመከራከር (ለመመካከር) ሳይሆን፣ መለስ ወስኖ የመጣበትን የሥራ ድርሻ ተቀብሎ ለመበተንና ሪፖርት ለመስማት የነበረው አሰራር፣ ዛሬ ተቀይሮ በርካታ የተነቃቁ ሚኒስትሮች የየራሳቸው ሃሳብ ተቀባይነት እንዲያገኝ (ለማንፀባረቅ) የሚታገሉበት መድረክ ወደ መሆን በመሸጋገሩ ነው፡፡ ይህም ሁናቴ ዋናውን የመንግስት ሥራ የመገምገም እና የማስፈፀም አቅምን ሳይቀር ከሚኒስትሮች ም/ቤት ወደ ኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ አሻግሮታል የሚያስብሉ ማሳያዎች አሉ፡፡ ይሁንና በዚህስብሰባ ላይም ቢሆን ደፈር ብሎ ከበረከት ስምዖን እና አባይ ፀሀዬ የተሻለ አዳዲስ ሃሳብ የሚያቀርብ ባለሥልጣን እንደሌለ ሰምቻለሁ (በነገራችን ላይ ምክንያቱን ባላውቅም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ‹የፖሊሲና ጥናት ምርምር አማካሪ› ተደርገው የተሾሙት በረከት ስምዖን፣ አባይ ፀሀዬ፣ ኩማ ደመቅሳ እና ዶ/ር ካሱ ኢላላ የሥራ ቦታቸው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት ሳይሆን መገናኛ አካባቢ በሚገኝ አንድ ህንፃ ላይ ነው፡፡ የተሰጣቸው ኃላፊነት ኃይለማርያምን በቅርብ እንዲያገኙ ከማስገደዱ እና በግልፅ ከሚታወቀው የአማካሪ አስፈላጊነት አኳያ ካየነው ግን ግራ የሚያጋባ ይመስለኛል)

አቶ አባይ ጸሐዬ

አቶ አባይ ጸሐዬ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ…

ኃይለማርያም ደሳለኝ ይህንን ቦታ ከያዘ በኋላ፣ ብዙዎች በስልጣኑ የማዘዝ አቅሙ ላይ አመኔታ እንደሌላቸው (አንጋፋ ታጋዮች እንደ ‹አሻንጉሊት› ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ) ደጋግመው መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ በግልባጩ ‹አፈንግጦ ለመውጣት መሞከሩ አይቀሬ ነው› የሚሉ ግምቶች ነበሩ፡፡ በርግጥ እነዚህ መላ-ምቶች ዛሬም ድረስ እልባት ባያገኙም፣ እዚህ ጋ ያልጠቀስኳቸው አንዳንድ ጉዳዮች ላይ ያሳያቸው ወጣ ያሉ አቋሞቹን ሳስተውል ግን፣ አሁን ያለው አሰላለፍ (የአነበረከት እና አባዱላ ፖለቲካዊ መጠናከር) ለእርሱም የተረፈው ይመስለኛል፡፡ እንዲሁም ከቤንች ማጂ የተባረሩ አማርኛ ተናጋሪዎችን አስመልክቶ በድርጅቱ ውስጥ ባልተለመደ መልኩ ‹አጥፊዎቹ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ› ከማለት አንስቶ (በነገራችን ላይ በአማካሪ ብዛት እንዲከበብ ካደረገው ምክንያት አንዱ ጓዶቹ በዚህ ንግግሩ መበሳጨታቸው ነው) በቅርቡ ህወሓትን ለመሸምገል በተዘጋጀ መድረክ ላይ ‹ሁኔታዎች እንዲህ እየተካረሩ ከሄዱ ወደ ማሰሩ መግባታችን አይቀርም› በማለት ማስፈራራቱ እና በቴዎድሮስ አድህኖም የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ላይ የመቆጣቱ ጉዳይ ድረስ የሚካተቱ እውነታዎች ሰውየው የራሱን መንገድ ለመከተል እየሞከረ መሆኑን ያሳያሉ ብዬ አስባለሁ፡፡

የሆነው ሆኖ እነዚህ ሁናቴዎች የፖለቲካውን ጉልበት ሙሉ በሙሉ በብአዴንና በተባባሪነት በጠቀስኳቸው የኦህዴድና ደህአዴን የአመራር አባላት አካባቢ ቢያከማቻቸውም፣ በማንኛውም ሰዓት ያሻውን ማድረግ የሚችለው የታጠቀው ኃይል ደግሞ ከህወሓት ጎን እንደተሰለፈ ይገኛል፡፡ መጪውን ጊዜም አዲስ ክስተት እንድንጠብቅ ገፊ ምክንያት ይህ አይነቱ የኃይል አሰላለፍ ይመስለኛል፡፡

ምን እንጠብቅ?

ከረጅሙ የፓርቲ ፖለቲካና መንግስታዊ መንገራገጮች በኋላ፣ የሁለቱንም የኃይል መሰረቶች ጠቅልሎ በመዳፉ ሥር የከተተው መለስ ዜናዊ በሞተ ማግስት ‹የኃይል መገዳደሮች ሊከሰቱ ይችላሉ› የሚለው የብዙዎቹ ግምት ነበር፤ ከወራት በፊት አስነብቤ በነበረው ከላይ በተጠቀሰው ፅሁፍም ግምቶቹ እውን መሆን እንደ ጀመሩ ማሳያዎች ማቅረቤ ይታወሳል፡፡ ኢህአዴግ ውስጥ ራሳቸውን ያቧደኑት ኃይሎች ዋነኛ ግብ ከሥልጣን የሚነሱ ጥቅሞችና አነስተኛ የየራሳቸው ፓርቲ ፍላጎቶች የፈጠሩት በመሆኑ፣ እንደ ሟቹ ደመ-ቀዝቃዛ አምባገነን አይነት በጠንካራ መዳፍ ሥር የሚያሰባስባቸው ባለመገኘቱ በየጊዜው የኃይል መሸጋሸጎች ሊከሰቱ እንዲችሉ አድርጓቸዋል፤ አሁንም እየተስተዋለ ያለው ይኸው እውነታ ነው፡፡ በዚህ አውድ ላይ ቆመን ሊፈጠሩ የሚችሉ የቢሆን ሃሳቦችን ስናስቀምጥም በጠረጴዛው ላይ የምናገኘው ሁለት ዕድሎችን ይመስለኛል፡፡

የመጀመሪያ ሲናሪዮ የሚሆነው ከላይ የጠቀስኩት ቡድንተኝነት እንዳለ ሊቀጥል ይችላል የሚል ነው፤ ይህም የሚሆንበት ምክንያት ባለኝ መረጃዎች መሰረት የፖለቲካውን መስመር የያዘው ቡድን መሪ አባላት፣ አሁን ያላቸውን መንግስታዊ ሥልጣን ጠብቀው መቆየትን መሰረታዊ መሰባሰቢያ አጀንዳ ማድረጋቸው ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የሳሞራና ጌታቸው ጥምረት ህወሓትን ወደ ቀደመው ዘመኑ ለመመለስ ቢሻም፣ ሊሄድበት የሚችልበት መንገድ አደገኛ መሆኑ (ወታደራዊ ላዕላይ መዋቅሩንና የደህንነት ኃይሉን ከመያዙ አኳያ) ሁኔታዎችን ባሉበት ይዞ መቀጠልን በትርፍ-ኪሳራ ስሌት የተሻለ አማራጭ አድርጎ ይወስደዋል ብዬ አስባለሁ፡፡
ሁለተኛው የቢሆን ዕድል፣ ዳግመኛ የኃይል መሸጋሸግ ሊፈጠር መቻሉ ነው፤ ሰዎቹ ጥቅመኛ በመሆናቸው የቋንቋ ተናጋሪነት ልዩነቶቻቸውንና የኋላ የመቆራቆስ ታሪኮቻቸውን ተሻግረው፣ አንዳቸው ከአንዳቸው ጋር ሌላ መልክ ያለው ስብስብ ሊፈጥሩ ይችሉ ይሆናል፤ ይህ አይነቱ አዲስ የኃይል አሰላለፍም፣ ከቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ በፊት በማይታወቀው ተሰዊና ሰዊ ሊጠናቀቅም ይችላል፡፡
በመጨረሻም ምንም ይፈጠር ምን፤ እኛን ሊያግባባን የሚገባው ጭብጥ፣ የትኛውም ቡድን በግንባሩ ውስጥ ቢነሳ፣ የማዕከላዊ መንግስቱን ህልውና ወደሚበታትን ሂደት መግባቱ ሊሰካለት አለመቻሉ ነው፤ ምክንያቱም በዚህ መልኩ ሄዶ የሚጣሉበትን ጠረጴዛ መስበሩ ምን እንደሚያስከትል ያውቁታልና ወደዚህ ምዕራፍ እንደማይሻገሩ አምናለሁ፡፡ ይሁንና ከፓርቲው ዝግነት እና ከፖለቲከኞቹ አቋም የለሽነት አንፃር አሁንም ሆነ በቀጣይ ጊዜያት ከማንም ግምት ውጪ ያሉ ክስተቶች እንደ ደራሽ ውሃ ድንገት ሳይታሰብ ግንባሩን ሊያተራምሱት ይችላሉ ብሎ መገመቱ አግባብ ይመስለኛል፡፡

Hiber Radio: በደቡብ ሱዳን የተከሰተው የጎሳ ግጭት በኢትዮጵያ እንዳይከሰት የሚመለከታቸው ሁሉ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ተጠየቀ

$
0
0

የህብር ሬዲዮ ታህሳስ 13 ቀን 2006 ፕሮግራም

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

<... ...>

አቶ ኤልያስ ወንድሙ የጸሐይ አሳታሚ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ ከሶስት ቀን በሁዋላ ለገበያ ስለሚቀርበው የሻምበል ፍቅረ ስላሴ > መጽሐፍ ከህብር ሬዲዮ ተጠይቆ ከሰጠው ማብራሪያ የተወሰደ ሙሉውን ያዳምጡት

> አቶ ኦባንግ ሜቶ ስለ ደቡብ ሱዳን የሰሞኑ ግጭት ለህብር ከሰጡት የተወሰደ

የሱዳኑ አልበሽር ኢትዮጵያና ኤርትራን በእርግጥ ለማስማማት ወይስ ሁለቱ መንግስታት በተቃዋሚዎቻቸው የሚደርስባቸውን ለመከላከል? እውነት ይስማማሉ? አቶ መለስ የሰጉበትን የጓዶአኤርትራን ፍላጎት ዕውን ሕወሃት ማሟላት ይችላል ? የተቃዋሚዎቹስ ሚና(ትንታኔ)

የኦባማ ኬር የመጀመሮያ ዙር ምዝገባ ሰኞ(ከአቶ ተካ ከለለ ጋር ከአትላኢታ ቲኪ ዲሴምበር 23 ይጠናቀቃል።…ኢንሹራንስ ያለውም ተመዝግቦ የገበያ አማራጩን ማየት አለበት? (ስለ ኦባማ ኬር ከአቶ ተካ ከለለ ጋር )

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

- በደቡብ ሱዳን የተከሰተው የጎሳ ግጭት በኢትዮጵያ እንዳይከሰት የሚመለከታቸው ሁሉ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ተጠየቀ

- ማንዴላን ያሰለጠኑት ኢትዮጵያዊ መኮንን ለቀብሩ ለመሔድ ቪዛ መከልከላቸውን በምሬት ገለጹ

- ኢትዮጵያ በደቡብ ሱዳን ጉዳይ እጇን እንዳታስገባ ተጠየቀ

- በጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ ላይ የተሰጠው የፍርድ ውሳኔ የዳኛው የእጅ ጽሑፍ ሳይሆን የሌላ ሰው መሆኑ ተገለጸ

- ምስጢሩ ሰኞ በርዮት የ30ኛ ወራት እስራት ይፋ ይሆናል

- በሳውዲ በሸሚሴ መጠለያ ያሉ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ አቀረቡ

- ከሳውዲ የመጡ እና በአገር ቤት ያሉ ወጣቶች ተፋጠዋል

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

በእስር ላይ የሚገኙት የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች መግለጫ በድምፃችን ይሰማ ይፋ ሆነ

$
0
0

በእስር ከሚገኙ የህዝበ ሙስሊሙ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የተሰጠ መግለጫ
ሰኞ ታህሳስ 14/2006

ኢትዮጵያ ከአንድ ሺህ አራት መቶ አመታት በፊት የ21ኛው ክፍለ ዘመን ማህበረሰብ ካሰፈነው ፍትህ የላቀ ፍትህ ማስፈን ችላ ነበር። የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉስ በነቢዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) አንደበት ‹‹በሐበሻ አንድም ሰው የማይበደልበት ንጉስ አለ›› ተብሎለታል። እንዲህ አይነት ፍትህ በዚህ መልኩ ለማስፈን ምን ያህል ፍትሀዊ፣ እውነተኛ እና የሰለጠነ ማህበረሰብ መገንባት እንደሚጠይቅ ግልፅ ነው። በሀገራችን የነበረው ፍትህ በጊዜው ነፃነት እና ፍትህ ፍለጋ ይዋትቱ የነበሩትን ማስጠለል የቻለ እና ዘመናትን ተሻጋሪ ነበር። ግና የዛሬው አሳዛኝ እውነታ ‹‹ሰዎች ስለ ፍትህ ግንዛቤ ባልነበራቸው በዚያ ዘመን የፍትህ ጥግ የደረሰችው አገራችን ሰዎች ሁሉ ወደ ዲሞክራሲ እና ፍትህ ፊታቸውን ሲያዞሩ ለምን ጀርባዋን ሰጠች?›› ብለን እንድንጠይቅ አስገዳጅ ሆኗል።
muslim1
ፍትህ ዘመን፣ ቦታና ሁኔታ የማይገድበው፣ በሃይማኖት፣ በሃገርና በብሔር ልዩነት የማይደረግበት፣ ሁሉም ለሁሉም እውን ሊያደርገው መጣር ያለበትና ሰው የመሆናችን ሚስጥር የሚፈታበት ጥልቅ እውነታ ነው። ግና ምድራዊም ሆነ ሰማያዊ ህጎች ፍትህን ቢደግፉትም ቅሉ በተጨባጩ ዓለም ግፍና በደል ተንሰራፍቶ ይገኛል። ቀደም ሲል አምባገነኖች በአደባባይ ይፈፅሙት የነበረውን ግፍ በዘመናችን ቅርፁን ቀይረው ፍትህ፣ ነፃነት እና እኩልነትን እየሰበኩ በተግባር ግን የህዝባቸውን ኑሮ የስቃይ ያደርጉታል።

መንግስት በሚዲያና በየስብሰባው ስለፍትህና ዴሞክራሲ በተደጋጋሚ ቢያነሳም መሬት ላይ ያለው ተጨበጭ ፍፁም ለማመን አዳጋች ነው፡፡ በማንኛውም ዘመን አምባገነኖች እንደሚያደርጉት ሁሉ ሰብዓዊነት የጐደለው ኢ-ፍትሃዊ ተግባር እየፈጸመ ሳለ ‹‹ህዝቡ ቦታ የሚሰጣቸው ሥነ-ምግባሮች፣ ህግጋትና መልካም እሴቶችን ለማስጠበቅ›› ሲባል የተሰራ እንደሆነ አድርጎ ለማቅረብ ይሞክራል። በመብት ትግላችን ሂደት ለሃይማኖታቸው ታማኝ በመሆን የፍትህና የነፃነት ጥያቄ ያነሱ ወገኖቻችን ሁሉ በመንግስት አካላት ስደት፣ እስራትና ሞት የደረሰባቸው ህብረተሰቡ የሚያከብራቸውን ስነ-ምግባሮች፣ እሴቶችና ህግጋት ሽፋን በማድረግ መሆኑ በእርግጥም ምጸት ነው።

ሙስሊሙ ህብረተሰብ ያነሳቸውና በወከላቸው ኮሚቴዎች አማካኝነት ለመንግስት ያቀረባቸው ጥያቄዎች ግልጽ፣ ቀላል፣ ሃይማኖታዊና ህገ-መንግስታዊ መብቶች መሆናቸውን መላው ኢትዮጵያዊና ዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ያውቀዋል። መንግስት ግን ለሰው እምነት ከባለቤቱ በላይ ተቆርቋሪ፣ ለሃገር ደህንነትና ሰላም የሚያስብ ብቸኛ አካል እና ህገ-መንግስቱን አክባሪና አስከባሪ እንደሆነ በመደስኮር የመብት ጥያቄያችንን የሀሰት ቅርፅ ሊያስይዘው ሞክሯል። በመሰረቱ መንግስት ኃይልና ጉልበት ያለው አካል ሆኖ ሳለ በተቃራኒው ደግሞ ህዝብ ጉልበት ስለሌለው ሰላምንና ደህንነትን አጥብቆ የሚፈልገው ከመንግስት በላይ ህዝብ ነው። ህገ-መንግስት ደግሞ መንግስት ያለውን ኃይል በመጠቀም ህዝብ ላይ ግፍ እንዳይፈፅም የሚገድብ ህግ እንደመሆኑ በመንግስት እንጂ በህዝብ ሊጣስ አይችልም።

ከጅምሩ መንግስት የሙስሊሙ የመብት ጥያቄ ከጀርባው ምንም ሴራ እንደሌለው የሚያውቅ መሆኑን ብንረዳም በአባላቱም ሆነ በማህበረሰቡ ላይ ብዥታ እንዳይፈጥር ዓላማችንን እና ጥያቄዎቻችንን ለሁሉም ግልፅ አድርገናል። ይህም ሆኖ ግን በተለያዩ ብሄሮችና ሃይማኖቶች መካከል መከባበር እንዲኖር የማድረግ ከፍተኛ ኃላፊነት ያለበት መንግስት ሙስሊሙን እርስ በእርስ፣ እንዲሁም ሙስሊሙን እና የሌላ ሀይማኖት ተከታዩን ህብረተሰብ ለግጭት የሚዳርጉ ተግባራትን ሲፈጽም ቆይቷል። አሁንም እያደረገ ይገኛል። ይህ አደገኛ አካሄድ ሊከሽፍ የቻለው በህዝባችን ብስለት እና ጨዋነት ብቻ ነው። ኩሩው የኢትዮጵያ ህዝብ ከህዝበ ሙስሊሙ የመብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የመረጠው በሳል አካሄድ ሊመሰገን የሚገባው ነበር። ይህ በሳል የህዝብ ምላሽ ሙስሊሙን እና ክርስቲያኑን ሊያጋጭ ይችል የነበረውን የመንግስት እንቅስቃሴ ቀልብሶ የህዝባችንን ጨዋነት፣ ተከባብሮ የመኖር ብቃት እና አስተዋይነት ዳግም ማሳየት ችሏል። ክስተቱም በታሪክ መዝገብ ውስጥ በወርቃማ ጽሁፍ የሚሰፍርበትና ለትውልድ የሚተረክበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።

በህዝበ ሙስሊሙ ላይ የፈጸማቸው በደሎች በህዝቡ ብስለት የከሸፉ ቢሆኑም ለህዝቡ ደንታ የሌለውና ስህተቱን አምኖ መቀበልን ውርደት አድርጐ የሚቆጥረው መንግስት ግን ህዝብ እየተቃወመው ህገወጥነቱን ቀጥሎበታል። በዚህም ምክንያት ‹‹መንግስት በሀይማኖታችን ጣልቃ አይግባብን! ያልመረጥናቸው ህገ-ወጥ የመጅሊስ አመራሮች ወርደው ፍትሀዊ ምርጫ ይካሄድ! የማናምንበት እምነት በግድ አይጫንብን!›› ብሎ የጠየቀውን ህዝብ ከነወኪሎቹ ለእስር፣ ለስደት፣ ለእንግልት እና ለሞት ዳርጓል።

የኢፌደሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 17 ንዑስ አንቀጽ 2 ‹‹ማንኛውም ሰው በህግ ከተደነገገው ስርዓት ውጪ ሊያዝ፣ ክስ ሳይቀርብበት ወይም ሳይፈረድበት ሊታሰር አይችልም›› ይላል። ነገር ግን ለፀጥታ ተግባር የተሰማሩት አካላት ህጉን በመጣስ ሰላማዊ ግለሰቦችን ሲይዙ የታጠቀ የጠላት ኃይል ላይ እንኳ ሊፈፀም የማይገባውን ግፍ፣ ድብደባ፣ ወከባ እና ስቃይ ይፈፅማሉ። ከፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ ሳያገኙና ለባለቤቱ ሳይሰጡ ያስራሉ። ህግ ጥሰው ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት በኋላ የግለሰቦች ቤት ላይ ብርበራ ያካሂዳሉ። በብርበራው ወቅት በሚፈጥሩት ሁከት በቤተሰብ ላይ ከፍተኛ ስጋት እና ድንጋጤ ይፈጥራሉ። ይህ ሁሉ የሚካሄደው ህዝቡ በፍርሃት ከመብት ጥያቄው ወደ ኋላ እንዲል ቢሆንም ውክቢያውና እንግልቱ ግን የመብት ጥያቄው ይበልጥ እንዲፋፋም፣ ህዝቡ ፍርሃቱ ለቅቆት ለነፃነት የሚከፈል መስዋዕትነት ያለውን ልዩ ጣዕም እንዲያጣጥም እና ሙሉ መብቱን ወደ መጠየቅ እንዲሸጋገር ነው ያደረገው።

የህገ-መንግስቱ አንቀጽ 18 ንዑስ አንቀፅ 1 ‹‹ማንኛውም ጭካኔ ከተሞላበት፣ ኢሰብዓዊ ከሆነ ወይም ክብርን ከሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት የመጠበቅ መብት አለው›› ይላል። ህገ-መንግስቱ ይህን ቢልም ዜጐች መሆናችንን ጥርጣሬ ውስጥ በሚከት መልኩ ከያዙን በኋላ በማእከላዊ በክረምት ቀርቶ በበጋ እንኳን ቅዝቃዜው በማይቻለው ‹‹ሳይቤሪያ›› ተብሎ በሚጠራው ጨለማ ክፍል ለ3 ወራት አጉረውናል። መቋቋም የሚያዳግተውን የማሰቃያ ስልታቸውን በመጠቀም ያላሰብነውንና ያልሰራነውን ‹‹እመኑ! ተናገሩ! ፈርሙ!›› ብለው አስገድደውናል።

ለቀጠሮ ፍርድ ቤት ስንቀርብ የደረሰብንን ሰቃይ አሳይተን ቢያንስ ፍርድ ቤቱ ስቃዩን እንዲያስቆምልን ጠይቀን ነበር። ያገኘነው ውጤት ግን ወደ ማዕከላዊ ስንመለስ ከመርማሪዎቹ በቀልና ተጨማሪ ስቃይ ነበር። ፍርድ ቤቱ የደረሰብንን ስቃይና የተከሰስንበትን ጉዳይ አግባብ እንዳልሆነ አይቶ ዋስትና ሰጥቶን ሳለ ፖሊስ የፍርድ ቤትን ትዕዛዝ ጥሶ ዋስትናውን በመከልከል ክስ መስርቶብናል። አሰቃዮቻችን ስለ ህገ-መንግስት እና መብት ስንናገር ‹‹ህገ-መንግስቱን ቀደህ ጣለው!›› እና ‹‹እኛ መሰዋዕትነት ከፍለን ነው እዚህ የመጣነው!›› ወ.ዘ.ተ በማለት ለህግም ሆነ ለሰው ክብር ደንታ እንደሌላቸው አሳይተውናል። ይህ ሁሉ መከራ በተቃራኒው ህገ-መንግስቱን ለማስከበር መታገል የሚያስፈልግበት ትክክለኛ ወቅት ላይ መሆናችን እንዲሰማን፣ እውነተኛ ፅናትና ወኔ እንዲኖረንም አድርጎናል።

በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 19 ንዑስ አንቀጽ 5 ‹‹የተያዙ ሰዎች በራሳቸው ላይ በማስረጃነት ሊቀርብ የሚችል የእምነት ቃል እንዲሰጡ፣ ወይም ማናቸውንም ማስረጃ እንዲያምኑ አይገደዱም። በማስገደድ የተገኘ ማስረጃ ተቀባይነት የለውም›› የሚለውን ድንጋጌ መሠረት በማድረግ እዚያው ማዕከላዊ የምርመራ እስር ቤት እያለን የደረሰብንን ስቃይና እንግልት ገልፀን ክስ አቅርበን ነበር። በምርመራ ጣቢያው ቃላችንን የሰጠነውም ሆነ የፈረምነው ተገደን መሆኑን ገልፀን ውድቅ እንዲደረግ ጠይቀናል። ሆኖም ግን ክሳችን ተዳፍኖ እና ተድበስብሶ እንዲቀር በመደረጉ በጊዜው ምላሽ ሳናገኝ ቀርተናል። ክስ ተመስርቶብን ወደ ከፍተኛው ፍርድ ቤት አቅርበን በኋላም በድጋሚ ጉዳዩን ያስረዳን ሲሆን አሁንም ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ሙሉ ለሙሉ የሚያደምጥበትንና ምላሽ የሚሰጥበትን ቀን እየተጠባበቅን እንገኛለን።

ከቤተሰብ፣ ከጠበቃና ከሀኪም ጋር እንዳንገናኝ አድርገው የፈፀሙብን የህግ-ጥሰት እና አስገድደው በማስፈረም እና ድምፅና ምስላችንን በመቅረፅ የፈፀሙብን በደል በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ቁጥር 424 መሰረት እስከ አስር አመት የሚያስቀጣ ኢ-ሰብዓዊ ተግባር ነው። ነገር ግን የፖሊሱም፣ የዐቃቤ ህጉም፣ የፍርድ ቤቱም አለቃ በሆነውና የፍትህ ስርዓቱን ሰብስቦ በያዘው ገዚው ፓርቲ አምባገነንነት በተቃራኒው እኛ ተከሳሾች ሆነን ጉዳያችን ‹‹በፍርድ ቤት›› በመታየት ላይ ይገኛል።

በማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ ስቃይ አድርሰውብናል። ከአስራ አራት ሰዓታት በላይ ያለ እረፍት ቀጥ ብለን እንድንቆም በማድረግ፣ ጀርባችን ሰንበር እስኪያወጣ እና እስኪገሸለጥ ራቁታችንን በሽቦ በመግረፍ፣ በሰንሰለት በማሰር እና ዓይናችንን በጨርቅ በመሸፈን የውስጥ እግራችን እስከሚላጥ ገልብጦ በመግረፍ፣ ቀንና ማታ አሰቃቂ በሆነ ምርመራ እና ድብደባ እንቅልፍ በመንሳት፣ ሃይማኖታችንንና ክብራችንን በመንካት፣ ፂማችንን በመንጨትና እንድንላጭ በማስገደድ፣ እንዲሁም ሰላት በመከልከል፣ ቤተሰብ፣ ጠበቃ፣ ሀኪምና የሃይማኖት አባት እንዳናገኝ በማድረግ፣ ከአቅም በላይ የሆነን ስፖርት በግድ በማሰራት፣ ብልት በመግረፍ፣ ‹‹ልጅህን እንገለዋለን! ሚስትህን አስረን በፊትህ ቶርች እናደርጋታለን! ብልትህ ላይ ሀይላንድ በማንጠልጠል መሀን እናደርግሃለን!›› ሲሉ በማስፈራራት ከፍተኛ የሆነ እንግልትና ስቃይ አድርሰውብናል።

ይህም አልበቃ ብሏቸው በሃገሪቱ የቅጣት ጣሪያ የመጨረሻ የሆነውን የወንጀል አንቀፅ ጠቅሰው ከሰሱን። ‹‹ህገ-መንግስት ይከበር!›› ብለን በጠየቅን ህገ-መንግስትን ለመናድ በመንቀሳቀስ ወነጀሉን። ተቃውሟችን ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ ሳለ ‹‹ከእኛ ውጪ ያሉ እምነቶች ከሃገሪቱ መጥፋት አለባቸው ብለዋል›› ሲሉ ከሰሱን። ሃይማኖታዊ የመብት ጥያቄያችንን ‹‹ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳ ነው›› በሚል ሊያጠለሹ ሞከሩ። ‹‹ህዝብ ያልመረጣቸው የመጅሊስ አመራሮች በህገ-ወጥ መንገድ መጥተው አይመሩንም! ፍትሀዊ ምርጫ ይካሄድ!›› ባልናቸው ‹‹መንግስት ይውረድ! መንግስት አያስተዳድረንም! ብለዋል›› በሚል ወነጀሉን።

ያዘጋጁት ክስ የህግ ባለሙያ ቀርቶ ማንም የህግ ግንዛቤ የሌለው ሰው በሚረዳው ደረጃ በህግ ስህተቶችና አመክኖአዊነት በጐደላቸው ሃሳቦች የተሞላ፣ በህግ ወንጀል ያልሆኑ አረፍተ ነገሮች እና ቃላት ወንጀል ተደርገው የተጠቀሱበት ፍፁም ተራ እና የሃገሪቷን የፍትህ ሁኔታ የሚያስገምት ክስ ነው። ምንም እንኳን ‹‹ክሱን ዳኞች ስርዓት ሊያስይዙት ይገባል›› በሚል የፀረ-ሽብር አዋጁን በመቃወም እና ክሱ ላይ ያሉ ስህተቶችን ሁሉ ነቅሰን በማውጣት የክስ መቃወሚያ ያቀረብን ቢሆንም የዳኞች ብይን ክሱን ይበልጥ የማይገባና ውስብስብ አደርጎታል።

ከታሰርን ጀምሮ የደረሱብን የህግ ጥሰቶች እና የፍትህ እጦቱ ከፍርድ ቤት ሂደት ራሳችንን ሙሉ ለሙሉ እንድናገል የሚገፉ ነበሩ። ሆኖም ግን የተወነጀልንበት ክስ ምን ያህል ከእውነት የራቀ፣ ጥያቄያችን ሃይማኖታዊ እና ህገ መንግስታዊ መሆኑን እና እንቅስቃሴያችንም ፍፁም ሰላማዊ እንደነበር ለህዝባችን በፍትህ አደባባይም ጭምር ለማሳየት ስንል የፍርድ ሂደቱ ውስጥ መግባቱ የተሻለ መሆኑን በማሰብ ሃሳባችንን ቀይረናል።

መንግስት በአግባቡ ሊተውነው ያልቻለውን አሳፋሪ የፍርድ ቤት ድራማውን ህዝብ እንዳያይበት ለመሸሸግ በመገደዱ ‹‹የተከሰሱ ሰዎች ክስ ከቀረበባቸው በኋላ ተገቢ በሆነ አጭር ጊዜ ውስጥ በመደበኛ ፍርድ ቤት ለህዝብ ግልፅ በሆነ ችሎት የመስማት መብት አላቸው›› የሚለውን ህገ-መንግስታዊ መብት በመጣስ ችሎቱ ዝግ እንዲሆን ተደርጎ ቆይቷል። በዝግ ችሎቱ የምስክር መስሚያ ጊዜ ብዙ አስገራሚ ድራማዎችን አይተናል። ዓቃቤ ህጎች ዳኞች የሚሰጡትን ብይን እንደማይቀበሉ እስከመግለጽ የደረሱበትን እና ምስክሮችን ማለት ያለባቸውን አሰልጥነዋቸው እንደሚያመጡ አምልጧቸው የተናገሩበትን አጋጣሚ ታዝበናል። በወቅቱ ‹‹ጋዜጠኞች፤ ዲፕሎማቶች እና ህዝባችን ምነው ይህንን አይተው በነበር?›› ብለን ከመመኘት ውጭ ምርጫ አልነበረንም።

ማንኛውም ታራሚም ሆነ ተጠርጣሪ በማረሚያ ቤት ሊያገኛቸው የሚገቡ በህግ የተደነገጉ መብቶች አሉ። መብቶች ግን እንደተለመደው ከወረቀት ዘለው መሬት ጠብ ማለት አልቻሉም። የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ላይ ሲሆን ደግሞ መብቶች በቅጣት ይተካሉ። ካለው የጋራ ችግር በተጨማሪ በእኛ ላይ በተለየ መልኩ በጥላቻ እና በበቀል ስሜት የደረሰብን እንግልት ህሊና ያለውን ሁሉ የሚጎዳ ነው። ከቤተሰቦቻችን መካከል ከጥቂቶች ጋር በስተቀር እንዳንገናኝ ተደርጓል። የምንጠየቅበትንም ሰዓት ከእስረኞች ሁሉ በመለየት በቀን ለሃያ ደቂቃ ብቻ እንዲሆን በማድረግ አድሎ እና መገለል ተፈፅሞብናል። በመካከላችን ልጆቹና ቤተሰቦቹ እንዳይጠይቁት የተደረገም አለ። ከሁሉም በላይ ከባድ ህመም ያለባቸው፤ ሆስፒታል ሄደው እንዲታከሙ የታዘዘላቸው፤ ቀዶ ጥገና እንዲደረግላቸው የተመራላቸው እና በማእከላዊ የደረሰባቸውን ድብደባ ለመታከም የጠየቁ ለዓመት ከአራት ወር በላይ መፍትሄ ሳያገኙ ስቃዩን ይዘው ‹‹የፍትህ ያለህ!›› እያሉ ይገኛሉ። ማረሚያ ቤት የደረሱብን እና እየደረሱብን ያሉ አድሎዎችንና እንግልቶችን ሁሉ ዘርዝረን ጉዳያችንን ለሚመለከተው ፍርድ ቤት ብናቀርብም የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች ፍርድ ቤት እንኳ ለመቅረብ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ሶስት ጊዜ ቀጠሮ አሳልፈዋል።

ሙስሊሙ ማህበረሰብ የመብት ጥያቄ እንቅስቃሴውን ከጀመረ በኋላ መንግስት በነጋዴውና በተማሪው፣ በመንግስት መዋቅር ውሰጥ በሚሰሩ አካላት፣ በሃይማኖት አባቶች እና በአስተማሪዎች፣ እንዲሁም በኢስላማዊ ተቋማት ላይ ሰብዓዊነት የጎደለው እና ህገ-መንግስቱን የሚጻረር የመብት ጥሰት መፈጸሙን ቀጥሎበታል። በበርካታ የክልል ከተሞችና ሙስሊሙ ደስታውን በሚገልጽበት የዒድ ዕለት በአዲስ አበባ ፈጽሞ ልንረሳው የማንችለውና ጭካኔ የተሞላበት ግፍ ፈጽሞብናል። የምንሳሳላቸው እና የምንወዳቸው ወገኖቻችንን እና ቤተሰቦቻችንን ለእስር፣ ለሞትና ለአካል ጉዳተኝነት ዳርጎብናል። ይህ ሁሉ ስቃይ እና መከራ በአንድ በኩል የመንግስትን ግፍ እና ለህግ ተገዢ አለመሆን ሲያጋልጥ በሌላ በኩል የህዝባችንን ፅናት እና ቁርጠኝነት አሳይቶናል። በየትኛውም ሃይማኖት፣ ባህል እና ልማድ ግፍ የተጠላ ሲሆን ለመብት ሲሉ መሰዋት ደግሞ ክብር ነው። ስለዚህ ለሃይማኖታችሁ፣ ለክብራችሁ እና ለደህንነታችሁ ለተሰደዳችሁ፣ ለታሰራችሁ፣ ለተደበደባችሁ እና ቤተሰቦቻችሁን ላጣችሁ ሁሉ ያለንን ክብር እንገልጻለን፤ በሀገራችን ለሚሰፍነው የሃይማኖቶች ነፃነት እና እኩልነት የመሰረት ድንጋይ የሚሆነው ዛሬ እናንተ የከፈላችሁት መስዋእትነት ነውና!

ለሁለት ዓመታት ያለ ምንም መሰላቸት እንግልቱ፣ ማስፈራሪያው፣ እስሩ፣ ድበደባው እና ግድያው ሳይበግራቸው እና ሰላማዊውን የተቃውሞ መስመር ሳይለቁ ለሃይማኖታቸው ያላቸውን ፍቅር ላሳዩ፣ እንዲሁም ይህን ድንቅ ታሪክ ለሰሩ አባቶች፣ የሃይማኖት መሪዎችና አስተማሪዎች /በተለይ ደግሞ ወጣቶች እና ሴቶች/ ያለንን ከፍ ያለ ክብር እና ምስጋና ልናቀርብ እንወዳለን። በሰራችሁት ሁሉ ተደስተናል፤ ኮርተንባችኋልም!

መንግስት የሃይማኖት ግጭት ለመፍጠር ያደረገውን ሙከራ ንቆ በመተውና ጉዳዩን በብስለትና በሰከነ መንፈስ በማየት፣ እንዲሁም እውነታውን ለመረዳት ጥረት በማድረግ ረገድ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፣ በተለይም ህዝበ ክርስትያኑ ላደረጋችሁት ትብብር ሳናመሰግን አናልፍም። በእውነቱ የሃይማኖት ልዩነት ሳያግደን በህዝብ ደረጃ ተከባብረን ስለመኖራችን ከተነሱ ምሳሌዎች ሁሉ በዚህ ሁለት ዓመት ውስጥ ያሳየነው መከባበር እና አንድነት ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው። ይህ ብሄራዊ አንድነት የበለጠ ተጠናክሮ በጋራ ለምንገነባት ሃገራችን ታላቅ ብርታት እንደሚሆን ጠንካራ እምነት አለን።

በተጨማሪም የፕሬስ ነፃነት በተነፈገበት ተጨባጭ የመብት ጥያቄያችንን እውነታ ለመገንዘብ ማስፈራሪያዎችን እና ዛቻዎችን አልፋችሁ፣ የመንግስትን የተሳሳተ እና ኢ-ህገመንግስታዊ አካሄድ ለይታችሁ ሂደታችን ላይ አዎንታዊ አስተያየቶች እና ገንቢ ትችቶችን ለሰጣችሁ ጋዜጠኞችና በሚዲያው ዘርፍ ለተሰማራችሁ ባለሙያዎች ሁሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

ወገኖቻችሁ ያጡትን ፍትህ እና ነጻነት በሃገራችሁ ለማየት በመጓጓት የበኩላችሁን አስተዋጽኦ ለማበርከት የምትጣጣሩ በስደት የምትገኙ ሙስሊሞችና የሌሎች ሀይማኖቶች ተከታይ ወገኖቻችን በሙሉ ላደረጋችሁት ሁሉ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው። በሀገር ውስጥ ለተጠናከረው የአጋርነት ስሜት የእናንተ አስተዋጽኦ የመጀመሪያውን ድርሻ ይይዛል።

በአጠቃላይ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ነጋዴው፣ አርሶ አደሩ፣ አርብቶ አደሩ፣ ተማሪው፣ ሴቱ፣ ወንዱ፣ ወጣቱ፣ አዛውንቱና ሌላውም፣ እንዲሁም በመንግስት መዋቅር ስር ሆናችሁ የመንግስትን የተሳሳተ አካሄድ ስትቃወሙ የነበራችሁ ዳኞች፣ ዓቃቤ ህጎች፣ አባቶች፣ ፖሊሶች፣ የጦር ሰራዊትና የፓርላማ አባላት በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርብላችኋለን። የጥረታችሁን ፍሬ በቅርቡ ያሳያችሁ ዘንድም አላህን እንለምናለን!

መልእክታችን

1/ በሙስሊሞች መካከል እና በሙስሊሙና በክርስትያኑ መካከል የታየውን አንድነትና መከባበር ሁላችንም በጋራ እንድንጠብቀው፣ እንዲሁም መሰረቱ የፀና ሆኖ እንዲቀጥል ለማድረግ እንድንጥር አደራ እንላለን። ሀገራችን ከእርስ በእርስ ሽኩቻዎች ወጥታ የእድገትና ብልጽግና ጉዞ እንድትጀምር ከተፈለገ ትክክለኛ የሃይማኖት ነፃነት፣ እኩልነት እና መከባበር በቅድሚያ እውን መሆኑ አማራጭ የሌለው ግዴታ ነው። የሃገራችንን እድገት የጋራ አላማ አድርገን፣ የጋራ ተጠቃሚ ሆነን መኖር የምንችለው ስጋትና ጥርጣሬውን በፍቅርና መተማመን ስንተካው ነው።

2/ በፅናት ሰላማዊ የመብት ትግሉን የምንቀጥል መሆኑንና የሚያስከፍለንን መስዋዕእትነት ሁሉ ለመክፈልም ዝግጁ መሆናችንን ለህዝባችንም ሆነ ለመንግስት መልእክት ለማስተላለፍ እንወዳለን። ለቀጣዩ ሰላማዊ የመብት ትግል እርከንም እኛም ህዝባችንም በሙሉ ዝግጅት ላይ መሆናችንንና ለመብታችን ተግተን ሰርተን መስዋዕት ከመሆን ወደኋላ የማንል መሆኑን ስንገልጽ በከፍተኛ ወኔ ተሞልተን ነው!

3/ መንግስት እየፈጸማቸው ያላቸውን ኢ-ህገ መንግስታዊ ተግባራት፣ በህዝበ ሙስሊሙ ላይ እየፈጸመ ያለውን እስራት፣ ግፍ፣ መስጂድ ነጠቃ፣ የሀሰት ውንጀላና የሃይማኖት ሰዎችን፣ ጋዜጠኞችንና የመብት ጠያቂዎችን በሽብርተኝነት መፈረጅና መሰል ህገ መንግስታዊ የመብት ጥሰቶችን በአስቸኳይ እንዲያቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን። በማእከላዊና በተለያዩ እስር ቤቶች የሚፈጸሙት ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች እንዲቆሙና የህሊና እስረኞችም መለቀቅ እንደሚገባቸው ለመግለጽ እንወዳለን። መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእውነተኛ ሰላም፣ ፍትህ፣ ዴሞክራሲ እና ልማት ባለቤት ሆኖ ማየት የዘወትር ህልማችን መሆኑንም ሳንገልጽ አናልፍም፡፡

በመጨረሻም በቃል ኪዳናችን ጸንተንና መነሻው ላይ ከነበረው በተሻለ ሁኔታ ተንቀሳቅሰን ፍጹም በሰለጠነና በተጠና መልኩ የተሟላ ፍትህ እና ነፃነት ለማግኘት በጽናት እና በቆራጥነት ሁሉም ባለድርሻ አካል እንቅስቃሴውን ከዳር እንዲያደርስ አደራ ለማለት እንወዳለን። የእንቅስቃሴው ማብቂያ ድልና ስኬት እንደሚሆን አንጠራጠርም!

አላሁ አክበር!

ግልባጭ፡- እዚሁ አገር ውስጥ እና በውጭ አገራት ለሚገኙ የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች

ከርዕዮት ዓለሙ ችሎት ጀርባ ያለው ጥቁር ዳኛ ማነው? – የሰነድ ማስረጃ የያዘ ጥብቅ ምስጢር

$
0
0

ከጋዜጠኛ ስለሺ ሐጎስ

ክፍል አንድ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥር አስር ቀን 2004 ዓ.ም በእነ ርዕዮት አለሙ ላይ ያስተላለፈው የጥፋተኝነት ውሳኔ በችሎቱ የተሰየሙት ዳኞች በነጻ ህሊና የሰጡት ፍርድ ነው ብሎ ያመነ ሰው አልነበረም፡፡ እዚህም እዚያም ሲወራ የነበረው ውሳኔው በመንግስት ፍላጎት ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነበር፡፡ ፕሮፌሰር መስፍንን ጨምሮ በርካታ ሰወች ይህንኑ በአደባባይ ጽፈውታል፡፡ ቆየት ብሎ ግን ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ የሚገልጹና ተጨማሪ ነገር ለማወቅ የሚገፋፉ መረጃዎች ወደኔ መምጣት ጀመሩ፡፡

እርግጥ የኢትየጵያ የፍትህ ስርአት በተደጋጋሚ ተፈትኖ የወደቀና ነጻነቱ ጥያቄ ውስጥ የገባ ከመሆኑ አንጻር እንዲህ አይነት የጥርጣሬ ድምጾች መሰማታቸው በራሱ ብዙ የሚገርም አይደለም፡፡ በመሆኑም በጉዳዩ ላይ የምር እንዳስብ የሆንኩት ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ በመስማቴ ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም ከዚያ በፊት በነበረው የፍርድ ሂደት ያስተዋልኳቸው ሦስት አጠራጣሪ ክስተቶቸ ናቸው እንደ ጋዜጠኛም ሆነ እንደ ርዕዮት የቅርብ ሰው ስለ ጉዳዩ ብዙ ለማወቅ እንድታትር የገፋፋኝ፡፡

የመጀመሪያው፣ ርዕዮት በማዕከላዊ ምርመራ ላይ እያለች የታዘብኩት ነው፡፡ ርዕዮት በተያዘች በማግስቱ አራዳ ፍርድ ቤት ቀርባ ፖሊስ የ28 ቀን የምርመራ ጊዜ ሲጠይቅ አባቷና ጠበቃዋ የሆኑት አቶ አለሙ ደግሞ ቤተሰብ እንዲጠይቃትና የህግ ምክር እንድታገኝ አመለከቱ፡፡ ዳኛዋም ፖሊስ ይህንኑ እንዲፈጽም አዘውና የ28 ቀን የምርመራ ጊዜ ሰጥተው ችሎቱ አበቃ፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ርዕዮት፣ ጠበቃም ሆነ ቤተሰብ ሳታገኝ 28ቱ ቀን አለፈ፡፡

የነበረው አማራጭ የቀጠሮው እለት ጠበቃዋ ገብተው ድጋሜ እንዲያመለክቱ ማድረግ ብቻ ነበር፡፡ እኛም ፍርድ ቤት ስትመጣ ጠብቀን ቢያንስ አይኗን ለማየት ጓጉተናል፡፡ በዕለቱ የሆነው ግን በጣም አስገራሚም አሳዛኝም ነበር፡፡

ቀጠሮው ከሰዓት በኋላ 8 ሰዓት ነበረ፡፡ በዚያን ዕለት ጠዋት 2፡30 ቁርስ ላደርስላት ወደ ማዕከላዊ ስሄድ ከዚያን ዕለት በፊትም ሆነ በኋላ አይቻት የማላውቃት አንዲት ልጅ “ርዕዮትን በሌሊት ወደ ፍርድ ቤት ወስደዋታል ሮጠህ ድረስባት” ብላኝ ካጠገቤ ብን አለች፡፡ ለአቶ አለሙ በስልክ ይህንኑ ነግሬ ወደ ፍርድ ቤቱ አመራሁ፡፡ ቦታው ቅርብ በመሆኑ 10 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ደረስኩ፡፡ እኔ ወደ ግቢው ስገባ ርዕዮት በፒካፕ መኪና ተጭና እየወጣች ነበር፡፡

የፍርድ ቤቱ የቀጠሮ ሰዓት የተለወጠው ባጋጣሚ ወይም በስህተት ሊሆን ይችላል በሚል ይህ ለምን እንደሆነ መዝገብ ቤቱን ጠይቀን የተረዳነው ኬዙን ያየችው ዳኛ በህመም ምክኒያት ለረጅም ጊዜ ስራ የምትገባው ከሰዓት በኋላ ብቻ መሆኑንና ሁኔታው ለእነሱም እንግዳ ነገር መሆኑን ነው፡፡ ስለዚህም የቀጠሮው ሰዓት ለውጥ በፖሊስ ፍላጎት ሆን ተብሎ ተፈጽሟል ለማለት ይቻላል፡፡ ይህ ማለት በፍርድ ቤቱና በፖሊስ መሀከል ሊኖር የሚገባው መስመር ላይ ችግር አለ ማለት ነው፡፡

ሌላው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለ5 ወራት ያህል ግራና ቀኙን ሲያከራክር ሰንብቶ ታህሳስ 17 2004 ዓ.ም የመጨረሻውን ፍርድ ለመስጠት በተሰየመበት ዕለት የነበረው ሁኔታ እንዲሁ ጥርጣሬውን የሚያጠናክር ነው፡፡ ቀጠሮው ከጠዋቱ 3፡00 የነበረ ቢሆንም በዚያን ዕለት ይሰጣል የተባለውን ፍርድ ለመስማት የተገኙ ሰዎች የችሎቱን አዳራሽ የሞሉት ቀደም ብለው ነበር፡፡ ዳኞቹ 1 ሰዓት አርፍደው 4፡00 ላይ ችሎቱ ተሰየመ፡፡ ወዲያውኑ ውሳኔው ማለቁንና ይሁን እንጂ በኮምፒውተር ተጽፎ ስላላለቀ ከሰዓት በኋላ እናርገው አሉ፡፡ በዚህ ጊዜ የእነውብሸት ጠበቃ አቶ ደርበው “ከሰዓት ሌላ ቀጠሮ ስላለኝ አልችልም” ብለው ከአራት ቀን በኋላ ለታሀሳስ 21 እንዲሆን አማራጭ አቀረቡ፡፡ ዳኛው ግን አልተቀበሉትም፡፡ “እነዚህ ሰወች ያሉት በማረሚያ ቤት ነው፤ ቀጠሮው ከሚራዘም 7 ሰዓት እንገናኝና እስከ 8፡00 እንጨርሳለን” የሚል አማራጭ አቅረቡና በዚሁ ተስማሙ፡፡

የዳኛው ንግግር የሆነ ጥሩ ነገር ሊኖር ይችላል የሚል ተስፋ ስላጫረብን ሁላችንም ከዚያው ሳንወጣ ሰዓቱ እስኪደርስ መንቆራጠጥ ያዝን፡፡

አይደርስ የለ ሰዓቱ ደርሶ ችሎቱ በሚሰየምበት አዳራሽ ተኮለኮልን፡፡ ዳኞቹ ግን በሰዓቱ የሉም፡፡ ግማሽ ሰዓት አለፈ፤ አልመጡም 8 ሰዓት ሲሆን ሁላችንም ቀጠሮ አለኝ ያሉትን ጠበቃ ደርበውን እያየን መሳቀቅ ያዝን፤ ሰዓቱ እየነጎደ ነው፤ 9 ሰዓት ሆነ፡፡ ዳኞቹም አልመጡም ጠበቃ ደርበውም አልሄዱም፡፡ 9፡45 ላይ ዳኞቹ መጡ፡፡ አቶ ደርበው ግን ቀሩ፡፡

ዳኛው ስለማርፈዳቸው ምንም ሳይሉ አሁንም ጽሁፉ ስላልደረሰ በሚል ተለዋጭ ቀጠሮ ለመስጠት አጀንዳቸውን ማገላበጥ ያዙ፡፡ “አራት ቀን ምን ሲደረግ ይራዘማል” ያሉት ዳኛ ከ23 ቀን በኋላ ለጥር 10 2006ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተው ዕለቱና ችሎቱ አበቃ፡፡ ተስፋችንም እንዲሁ፡፡

ይህ ሁኔታ አንዳች ደስ የማይል ነገር እየተከናወነ እንዳለ የሚናገር መሆኑ እንዳለ ሆኖ ቀደም ሲል ያነሳነውን ጥርጣሬ ወደ እውነት የሚገፋው ተጨማሪ ክስተት፣ ለቀጠሮው መራዘም ምክኒያት ሆኖ የቀረበው ነገር ነው፡፡ የታህሳስ 17ቱ ቀጠሮ ወደ ጥር 10 የተሻገረው ውሳኔው በኮምፒውተር ተጽፎ አለማለቁ ሆኖ ሳለ ዳኛው ጥር 10 ያነበቡት በኮምፒውተር ያልተተየበ የእጅ ጽሁፍ ነበር፡፡ ስለዚህም የቀጠሮ ለውጡ የተካሄደው ከችሎቱ ጀርባ ባለ ሌላ ምክኒያት እንጂ ዳኛው እንዳሉት የኮምፒውተር ጽሁፍ ጉዳይ አይደለም ለማለት ይቻላል፡፡

እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎችም ትንንሽ የሚመስሉ በርካታ ትዝብቶች ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ ከሚገልጸው መረጃ ጋር ተደምረው ሲታዩ የሚሰጡትን ትርጓሜ በማስረጃ ለማረጋገጥ መጠነኛ ጥረቶች ተደርገዋል፡፡

ይህን ለማረጋገጥ ሁነኛና ቀላል ዘዴ ሊሆን የሚችለው በእለቱ ዳኛው ያነበበውን የእጅ ጽሁፍና የዳኛውን ትክክለኛ የእጅ ጽሁፍ አግኝቶ ማመሳሰል ነው፡፡ በዚሁ መሰረት ይህን ለማድረግ የሚያስችሉ ማስረጃዎች ተገኝተዋል፡፡ ማስረጃዎቹ ዳኛው በዕለቱ ያነበበው ጽሁፍ በራሱ በዳኛው የተጻፈ አለመሆኑን የሚያሳዩ ናቸው፡፡

ቀጣዮቹን ሁለት ምስሎች ይመልከቱ
reyot alemu 1

reyot alemu 2

ኢትዮጵያ የጋራችን ኤርትራ የግላችን! “ከ 40 ግድብ አንድ የአሰብ ወደብ” –ከሰመረ አለሙ

$
0
0

ኤርትራዉያኖች ተበልጠዉ በኢትዮጵያ ተንደላቅቀዉ የሚኖሩበትን ሁኔታ ከተነጠቁ በሗላ እንደገና እጃቸዉ ለማስገባት በተለያየ ዘዴ ቢጠቀሙም ህዋአት እና ሻቢያ “እባብ ለባብ ይተያያል ካብ ለካብ” አይነት ሆነና ኤርትራዉያን የፈለጉትን ያህል ሳይሆንላቸዉ ቀርቶ እዚሀ ላይ ተደረሷል። የጸሀየ ግብአተ መሬት ፉከራ ከከሸፈ በሗላ ኤርትራዉያን ኢትዮጵያን ሊበትንልን ይችላል የሚሉትን ሀይል እና ዘዴ ቢበደሩም መላ ቢመቱም ቢያሰባስቡ እና ቢያሰለጥኑም፤ የኢትዮጵያ አንድነት ፍንክች ሳይል ቀርቶ እዚህ ላይ ይገኛል። የኤርትራ ምሁራን ኢትዮጵያ ያስተማረቻቸዉ ተራ ወርደዉ የሚያስገምት ጽሁፍ ቢጽፉም፤ በቀይ ባህር ማተሚያ ቤት የእዉሸት ፋብሪካቸዉ ተረት መሰል የኢትዮጵያ ታሪክ ቢያሳትሙም፤ ቅጥፈት የተሞላዉ ወረቀት ቢጽፉም ድካማቸዉ ሁሉ ያለምንም ፍሬ ልፋት ብቻ ሁኖ ቀርቷል
ታድያ ለሁሉም ብልሀት አለዉ እንዲሉ ይህ ዘዴ ያለመስራቱን የተረዱ ኤርትራዉያን አቶ መለስንና ለኤርትራ ስስ ልብ ያላቸዉን የህወአት ባለስልጣኖች በመጠቀም ዛሬም ከዜጋዉ በላይ የኢትዮጵያን በረከት እየተጎናጸፉ ይገኛሉ። በተለይ ከአቦይ ስብሀት አለንላችሁ መግለጫ በሗላ ብዙ ኤርትራዉያን ባላቸዉ ንክኪ አማካኝነት በብዛት ወደ ሀገር ጎርፈዋል ከኢትዮጵያ ሳይባረሩ የቀሩትን ወገኖቻቸዉንና በዉጭ ሀገር በሚኖሩ ኤርትራዉያን አማካይነት የዉስጥ ለዉስጥ ግንኙነታቸዉን በማጠናከር ኢትዮጵያ ዉስጥ የቀድሞ ቦታቸዉን ይዘዋል።
በቅርቡ በወጣዉ ጽሁፍ ወደ 1700 የሚሆኑ የኤርትራ ተወላጆች ከኢትዮጵያዉያን ወጣቶች በላይ ቅድሚያ ተሰጥቷቸዉ ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ጎርፈዋል ይህ አፊሲያላዊ ቁጥር ነዉ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ ቁጥር እንዳላቸዉ እማኝነት ያላቸዉ ዜጎች በቁጭት ይገልጻሉ። እንግዲህ ልብ ይበሉ እንደ አይን ብሌን በምናያቸዉ የትምህርት ተቋማት ኢትዮጵያዊዉ ወጣት በጫት የቀን ህልም ሲያልም ትላንት ኢትዮጵያ ላይ የተኮሱ ዛሬም ለኢትዮጵያ ክብር እና ፍቅር የሌላቸዉ ኤርትራዉያን በኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ሲማሩ በእጂጉ ያሳዝናል።እነሱ እንዲማሩ ሌላዉ ኢትዮጵያዊዉ ቦታዉን ለነሱ መልቀቅ አለበት ማለት ነዉ።
ethiopias-planned-renaissance-damይህ በትምህርት ዘርፍ የተገኘዉ መረጃ ነዉ። በንግድ፤እርሻ፤ፐሮፐርቲን በተመለከተ ከሀገሬዉ ነዋሪ በላይ እዛ ያሉትም ከኤርትራ፤ከአዉሮፓ እና አሚሪካ እየጎረፉም በከፍተኛ ሁኔታ በመጠቀም፤በመጠቃቀም፤ከባንክ በመበደር እና በማምታት ህገ ወጥ ጥቅም በማግኘት ላይ ይገኛሉ። ገንዘብ ማሸጋገር ዋናዉ አገር መጉጃቸዉ ነዉ በዚህም ሂደት ገንዘብ አገሩን እየለቀቀ በባህር ማዶ ባንክ እና በዉጭ ሀገር ኢንቨስትመንት ላይ ይዉላል። እነሱም በዚህ ህገ ወጥ ስራ አንድም ጠላታቸዉ ኢትዮጵያን ይጎዳሉ አንድም ትርፋቸዉን ያደልባሉ። በህጋዊ መንገድ ቀረጥ ከፍለዉ ከመስራት ይልቅ ህገወጥ የሆነዉ መንገድ ባያተርፋቸዉም ይመርጡታል።
የሚያሳዝነዉና አንጀት የሚያበግነዉ እኛዉ መሀል ስንት ቤት ሰርተሀል? ሰሞኑን ምን ልከሀል? ትንሺ ገንዘብ ሰጥተህ በትግራይ በኩል ዘመድህን አስመጣ እያሉ በድፍረት ሲያወሩ በጣም ልብ ይሰብራል። ይህች ሀገር መች ነዉ ለዜጎቿ የምትሆነዉ? መች ነዉ ዜጎቿን የምታከብረዉ? መች ነዉ ዜጋዉ ከእንደዚህ አይነት ጥቃት ድኖ ሀገሩ የእርሱ መሆኑን የሚረዳዉ ብዬ አንዳንዴ እራሴን እጠይቃለሁ። እንደዉም ደግሞ የድፍረት ድፍረት ከህዋአት ጭቆናም ነጻም የሚያወጡን እነሱ ሁነዉ ተገኝተዋል ጆሮ የማይሰማዉ የለ። የአለሙ ሚዲያ አምነስቲ ኢንትርናሽናልን ጨምሮ በወር 3000 ኤርትራዊ አገሩን ይለቃል ሲባል አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ከህዝቡ ፍቅር የተነሳ ያለ አጃቢ ነዉ የሚሄዱት ብለዉ ተቃዋሚዎቻችንን ሊያሳምኑን ይከጂላቸዋል ታዲያ ይህ ሁሉ ፍልሰት ነጻነት ፍለጋ ካልሆነ ፍለሰቱ አድቬንቸር ነዉ ማለት ነዉ ወይስ አቶ መለስ እንዳሉት ኤርትራዉያን እግር እንጂ አገር የላቸዉም የሚባለዉ አባባል እዉነት ሊሆን ነዉ?
በመሰረቱ አፍቃሪ ኢትዮጵያ ኤርትራዉያን ኢትዮጵያ ዉስጥ መኖራቸዉ ቅር የሚለኝ ሰዉ አይደለሁም ባለፈዉ ጽሁፌም እንደገለጽኩት ሀገሪቱ ዛሬ በስልጣን ላይ ቁጭ ብለዉ ከገደሏት በላይ ለሀገራቸዉ ኢትዮጵያም የሞቱ ታላላቅ የኤርትራ ተወላጆችንም ገልጫለሁ ምንም እንኳን ዛሬ በህይወት ባይኖሩም ለነሱ ያለኝ አድናቆትና ክብር ከጊዜዉ ጋር የሚደበዝዝ አይሆንም። እኔም የምኖረዉ በዉጭ ሀገር ነዉ ልዩነቱ እኔ ዛሬ የምኖርበትን ሀገር በክብር እና በፍቅር የማገለግል ነኝ በሀገሩ ተጠቃሚ ሁኜ ለሀገሩ ጥፋት የምመኝ አይደለሁም። ይህ ነዉ የእኔና የዘመኑ ኤርትራዉያን ልዩነት።
ዛሬ ሰዉ ምን ይለኛልም ቀርቶ ኤርትራዉያን በግላጭ ኢትዮጵያ የጋራችን ኤርትራ የግላችን፤ የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ የሚል ፌዝ የሚመስል ፌዝ ያልሆነ ቋንቋ በብዛት ሲጠቀሙ ይሰተዋላሉ። የሚገርመዉ ሀገር ዉስጥ ኑሮዉን ዘርግቶ የሚገኘዉ ኤርትራዊ ወይም ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ በፍልሰት የሚገባዉ ኤርትራዊ ስለ አሰብ ምን ታስባለህ ስለ ባድሜ ምን ታስባለህ ተብሎ ቢጠየቅ መልሱ ለማያዉቃት፤ ላልኖረባት ፤ ላልተጠቀመባት፤ ለተንገላታባት አገሩ ኤርትራ ነዉ።

ኤርትራዉያን ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዉያን ሰፈር እንዴት ተንሸራተዉ እንደገቡ ግንዛቤ ቢያስፈልግ አንድም የህዋት ንክኪያቸዉን በመጠቀም፤ማንነታቸዉን በመለወጥ ሲሆን ሌላዉ ደግሞ በግንዛቤ የተጎዳዉን ኢትዮጵያዊ እየመረጡ በመጠቀም ነዉ። አንበሳዉ አለማየሁ መሰለንማ ማን ይደፍረዋል ተጠቃሚዉን ይጠቀምበታል እንጂ። እንግዲህ ወደፊት በስፋት ብመለስበትም ጀግና በጠፋበት ዘመን እንደ ቀድሞቹ ጀግኖች አያቶቹ በጠላት ሜዳ ተረማምዶ ግዳይ ጥሎ የቁርጥ ቀን ሲመጣ ኢትዮጵያዊነት ምን ማለት እንደሆነ አስመስክሮ ኢትዮጵያዉያን ሰፈር እንደገና የተሀድሶ መንፈስ ለሰጠዉ አለማየሁ መሰለ በያለንበት ዋንጫችንን እንድናነሳ በትህትና እጠይቃለሁ ገድሉም ከጊዜዉ ጋር ሊደበዝዝ አይገባም። በእዉነቱ አለማየሁ ያነን የመሰል ገድል ሲሰራ ዉቅያኖስ ጠልቆ ዉሀ ሳይነካዉ እንደወጣ ዋናተኛ ነዉ የምቆጥረዉ። ከጀብድ ስራዉ በላይ ደግሞ ንግግሩ የቀድሞዎቹ አንበሶች አያቶቹን መንፈስ የሚያንጸባርቅ ነበር። አለማየሁ በአንድ ቃለ መጠይቅ “ተስፋዬ ምንም እንኳን የሻቢያ ሰላይ ቢሆንም እኛም ከእሱ በላይ መስራት እንችላለን በሚል ጽኑ ኢትዮጵያዊ መንፈስ ስራዬን ተያያዝኩት” ነበር ያለዉ። ቆፍጣናዉ አለማየሁ በእዉነት የዘመናችን በላይ ዘለቀ ቢባል ብዙም ማጋነን አይሆንም ሰዉ የሚለካዉ እንደየዘመኑ ነዉና።

ኢትዮጵያ ጥንታዊ እና ገናና አገር ነች በዚህ በረጂም ዘመኗ ረጅም ስርን ተክላለች በረጂም ዘመኗም ብዙ ጠቃሚ እዉቀቶችን፤እምነቶችን፤መረጃዎችን ለዜጎቿ እና ለአለም አበርክታለች ከዚህ እና ከሌላም ስንነሳ ኢትዮጵያ እንደሀገር ኢትዮጵያዉያንም እንደተከበረ ዜጋ በቀጣይነት መኖር አለባቸዉ። ኢትዮጵያ ትላንት በግርግር እንደተፈጠረች ሁሉ አንዳንድ ብሄረተኞች አንድም የበታችነት መንፈስ በተጠናወታቸዉ በሌላም በባእድ ሀይሎች እየተገፉ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዉያንን ለመፈታተን የሚያደርጉት ጥረት ያለ ይሉኝታ ሊመከት ይገባል እላለሁ።
እንግዲህ እንዲህ ያለዉን አልፎ ሂያጅ የግርግር መንፈስ ሳይበግረዉ በእዉቀቱ ስዩም እንዳለዉ ወጣቱ ኢትዮጵያ አገሩን ከአባቶቹ በበለጠ ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ማድረስ ይገባዋል እላለሁ። ዛሬ እንዲህ አደርግልሀለሁ እንዲህ ብናደርግ የምድር መንግስተ ሰማያት እንኖራለን በሚል ቀቢጸ ተስፋ የሰፈሮቻቸዉን ልጆች እያማለሉ ኢትዮጵያዊነት ላይ ወገኖችን የሚያስኮርፉ ነገ ሀሳባቸዉ ተሟልቶ እነሱ ኢትዮጵያን ቢከፋፈሉ እንደ ደሀ አጥር ሁሉም እየጣሳቸዉ ይሄዳል እንጂ እነሱም ተጠቃሚ እንደማይሆኑ በልምምጥ ሳይሆን በድፍረት ሊነገራቸዉ ይገባል። ፍቅርን የሚያዉቅ ጀግና ብቻ ነዉ እነሱ ግን ፍቅርን ልምምጥ ያደርጉታል። እነሱን ትልቅ ያደረገ እንዲህ የማኩረፍ ነጻነት ሁሉ የሰጣቸዉ ኢትዮጵያዊነት ነዉ። በአንድ ወቅት ፕሮፌሰር ጌታቸዉ ሐይሌ የዘረኞች እብሪት ሲበዛ አይተዉ ለአንዱ ዘረኛ በሰጡት መልስ ምንሊክ ባይሰበስቡህ እራስህን አንዱ የጎረቤት አገር ታገኝዉ ነበር ያሉት ዛሬም በባዶ ሜዳ ለሚያብዱ ነገር ለጠፋባቸዉ ዘረኞች በግልጽ ሊነገር ይገባል እላለሁ። እነዚህ የምንሊክን ታላቅ ስራ የማያዉቁ ደካሞች ምንሊክ ባይሰበስቧቸዉ ስማቸዉ ሌንጮ/ሀጎስ/ጫላ/ለማ… ከመሆን ይልቅ ሪካርዶ/ሮበርት/ዴቢድ ሲሆን ሀይማኖትም በልካቸዉ ይሰፋላቸዉ ነበር። የሚያሳዝነዉ የፕሮፌሰሩ ጽሁፍ ከግማሽ ቀን በላይ በድረ ገጾች ላይ አልዋለም ምክንያቱም የታወቀ ነበር።
እዚህ ላይ ላልፈዉ የማልፈልገዉ ስለ ታላቁ የኦሮሞ ህዝብ በኢሳይያስ ታግተዉ ጻፉ በሚባሉ ዘረኞች በነ አስመሮም ለገሰና 12ኛ ክፍል ባልጨረሰ መሀይም ተጽፎ ለንባብ ሲበቃ ማየት በእጅጉ ያሳዝናል ዛሬ በኢትዮጵያ ምስረታ በኢትዮጵያ ስነጥበብ በኢትዮጵያ አስተዳደር የኦሮሞ አሻራ ያላረፈበት አንድም ነገር አይገኝም። በሀገር እና ከሀገር ዉጭ ታላላቅ የኦሮሞ ጠቢባን ባሉበት አለም ስለ ኦሮሞ ህዝብ ታላቅነት፤በደል፤ጭቆና ከኤርትራ ኤክስፖርት ሲደረግ ከምንም በላይ የሚያሳፍረዉና የሚያዋርደዉ የኦሮሞን ህዝብ እንጂ ሌላዉን አይሆንም። የኦሮሞ ህዝብ ሞግዚት የሚያስፈልገዉም አይደለም የኦሮሞ ህዘብ በደሉን እና ጥቅሙን በሚገባ ያገናዝባል የኦሮሞ ህዝብ ህመም ከአማራዉ፤ጉራጌዉ፤ወላይታዉ…. በላይ እነ አስመሮም ለገሰንና ተስፋዬ ገ/አብን ለምን እንዳመማቸዉ ነገሩ ግልጽ ነዉ እነሱን ያቃታቸዉን ሀይል እነሱ እንዲሞክሩላቸዉ ታስቦ ነዉ ታዲያ ኦሮሞ ይህን አጣ? የምን ንቀት ነዉ? ከኦሮሞ እና አማራዉ የተወለደ 10 ሚሊዮን ህዝብ ከመኖሩም በላይ የአንዱን ደም አጥርቶ አንተ ከዚህ ነህ አንተ ከዚያ ነህ የሚያሰኝ ሁኔታም አይኖርም። አሁንም የኦሮሞን ህዝብ አታላግጡበት አርፋችሁ ቁጭ በሉ ሊባሉ ይገባል። ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ምነዉ ተስፋዬ ገ/አብ ከኦሮሞ በላይ ኦሮሞ ሆነ ያሉት እነ አስመሮም ለገሰን አፍ አዘግቶ እዛዉ እስር ቤታቸዉ ሊያስቀምጣቸዉ በቻለ ነበር ታድያ እነሱ ለክብር ስላልተፈጠሩ በተቻላቸዉ መጠን ቶሎ ትርፍ ያመጣልናል ብለዉ የሚሉትን ብቻ መሞከር ስለሆነ ሊማሩ አይችሉም። እንደ እዉነቱ ከሆነ በዛሬዉ አለማችን ከማንም በላይ በባርነት ቀምበር ስር ያለ ህዝብ ቢኖር ኤርተራዊ በመሆኑ ፍትህ እና ዲሞክራሲ ካማራቸዉ እዛዉ በእስር ቤት የሚኖረዉ ህዝባቸዉንና እራሳቸዉን ነጻ እንዲያወጡ ይጠየቃሉ ለዛም ካልታደሉ ተራ የኢሳይያስ ካድሬ መሆናቸዉ ቀርቶ በክብር እንዲቀመጡ እናሳስባለን 90 ሚሊዮን ህዝብን መናቅ የጤንነት አይመስልም።
ለማጠቃለል በስልጣን ላይ የተቀመጡት ህዋቶች በአቶ መለስ ምንጠራ አክራሪ ትግሬዎች ተነስተዉ በአብዛኛዉ ኤርትራ እና አፍቃሪ ኤርትራዉያን ቦታዉን በመያዛቸዉ የትግራይ ወንድሞቻችን ነገ ከሚመጣዉ ጥፋት እራሳቸዉን ለመከለከል ከወገናቸዉ ጋር ሰልፍ እንዲቆሙ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ። ትላንት የትግራይ ወንድሞቻችንን ነፃ ለማዉጣት፤ የትግራይ ክልል ባድሜ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ድምበሮች እንዲከበሩ በዛ የፈሰሰዉ ደም ከንቱ ሁኖ ቀርቷል። ባድሜም ለኤርትራ ሊመለስ ዉስጥ ለዉስጥ ዲፕሎማሲዉ ተጧጡፏል ኤርትራዉያንም ያለምንም ችግር በኢትዮጵያ የቀድሞ ቦታቸዉን በመያዝ ላይ ናቸዉ። ትላንት የትግራይ ህጻናትን በቦምብ የፈጀ ሀይል ዛሬ ለትግራይ ህዝብ ወዳጂ የሚያደርገዉ ምንም ነገር ሊኖር አይችልም ህዝቡም አስተዳደሩም ትላንት የነበረ ነዉና። የኢትዮጵያም ህዘብ በችግሩ ጊዜ የችግሩ ተካፋይ ካልሆናችሁ የችግራችሁ ጊዜ ብቻ ድረሱልን ብትሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ደግነቱና እርዳታዉ ቀጣይነት ሊኖረዉ ስለማይችል ካሁኑ ማሰብ አግባብ ነዉ እላለሁ።

እንግዲህ በእነ ገበየሁ ባልቻ፤በላይ ዘለቀ፤በላይ ቃለአብ፤ኡመር ሰመታን፤ታከለ ገ/ሀዋያት፤አብዲሳ አጋ በነ አፈወርቅ ወ/ሰማያት እና ዛሬ ደግሞ እንደ ጎሹ ወልዴን

አለማየሁ መሰለን የመሰሉ ጀግኖቻችን ባሉበት አገር ወገን ዉርድተን መቀበል በእጂጉ ይከብደዋል። እንግዲህ የተኛዉ ወገን ነቃ ብሎ እንዲጠበቅ መሰሪዎችም እንዲጠነቀቁ ያህል ነዉ እንጂ ምን ያልተጻፈ አለ ሰሚ፤ አንባቢና አገናዛቢ ከተገኘ። ይህችን ጽሁፍ ከከተብኩ በሗላ በህዋትና በሻቢያ መሀከል በራቸዉን ዘግተዉ ኢትዮጵያንን አግልለዉ ከዚህ በፊት እንዳደረጉት ሁሉ በተዋራጅነት የሚያስቀምጥ አንዳንድ ድርድሮችን በማድረግ ላይ እንደሆኑ ጠቋሚ ጽሁፎች በብዛት ተሰራጭተዋል። ኤርትራ ኢትዮጵያ ኮሚቴም የሚባል የማወናበጃ ስብስብም በየቦታዉ እንደ አሸን ብቅ በቅ እያለ ነዉ። ብዙ ለግላጋ የኢትዮጵያ ህጻናት ያለቁበት የትግራይ ከልል ባድሜም በተዋራጂነት ለኢሳይያስ አፈወርቅ በእጅ መንሻነት ህዋአት ሊያስረክበዉ እንደሆነ ይገመታል። እንግዲህ ይህንና ሌላዉን አጠቃለን ስንመለከተዉ ኳሷ ያለችዉ የትግራይ ወንድሞቻችንን ክልል ስለ ሆነ ወደ ወገናቸዉ ተጠግተዉ የሚጠበቅባቸዉን ግዴታ እንዲወጡ አሳስባለሁ ለራሳቸዉም ጥቅም ሲባል። ከላይ እንደገለጽኩት የህጻናት ትምህርት ቤት በቦምብ ያጋየ ለትግራይ ህዝብ ወደፊት ወዳጂ ይሆናል የሚል እምነት ስለሌለኝ ከህዋአት ዉጭ ማሰብ እንዲችሉ በድጋሚ አሳስባለሁ።
እስከዛዉ በቸር ይግጠመን ሰመረ አለሙ ነኝ ከባህር ማዶ መልካም የፈረንጂ ገና
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live