Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

Health: “ባለቤቴ እንደምትወደኝ አውቃለሁ፤ የወሲብ ፍላጎት ግን የላትም፤ በዚህ የተነሳ ትዳሬ አደጋ ላይ ነው”

$
0
0

በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 58 ላይ ታትሞ የወጣ

ባለትዳር ነኝ፡፡ ከባለቤቴ ጋር ትዳር የመሰረትነው ከዩኒቨርሲቲ ተመርቀን ስራ እንደጀመርን ነበር፡፡ ባለቤቴ እጅግ ሲበዛ ዝምተኛ፤ እና አይን አፋር ነች፡፡ በታማኝት እና በፍቅር በቆየንባቸው ዓመታት ‹‹ከጋብቻ በፊት ወሲብ መፈፀም የለብንም›› የሚል አቋም ስለነበራት እስከምንጋባ ድረስ ቃሏን ጠብቄ ቆይቻለሁ፡፡ ወደ ትዳር ከገባን በኋላ ግን ባለቤቴ ወሲብ ለመፈፀም ያላት ፍላጎት እጅግ አነስተኛ ነው፡፡ ወሲብ ከመፈፀም በኋላ የደስታን ስሜት ሳይሆን የመከፋት መንፈስ ነው የሚታይባት፡፡ ወደ ትዳር እንደገባን ባሉት አንድ እና ሁለት ዓመታት ጥሩ የሚባል የትዳር እና ፍቅር ጊዜ የነበረን ቢሆንም ወሲባዊ ህይወትን ግን ከጀመርን በኋላ አስደሳች እና ጣፋጭ ባለመሆኑ የተነሳ ሁልጊዜ አዝን ነበረ፡፡ ከዚያ በኋላ ባሉት ዓመታትም ከቀን ወደ ቀን የባለቤቴ የወሲብ ፍላጎት መቀነስ እና ደስተኛ አለመሆን እያሳሰበኝ መጥቷል፡፡ በትዳራችንም ላይ የመቀዛቀዝ ስሜትን ፈጥሯል፡፡ አንድ ነገር በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ፤ እኔ እንደምወዳት ሁሉ እሷም ትወደኛለች፡፡ የተፈጠረባት የወሲብ ፍላጎት መቀነስ ችግርን በተመለከተ በግልፅ ለማውራት ፍቃደኝነት ብዙም አይታይባትም፡፡ የወሲብ ጥያቄ ገና በማነሳባት ወቅት የመረበሽ፣ የመደንገጥ እና የመፍራት ስሜትን ስለምታንፀባርቅ እኔም እረበሻለሁ፡፡ በአንድ ጊዜም ፍላጎቱን አጣዋለሁ፡፡ የነገሩ መደራረብ እና መደጋገም እኔን ከትዳሬ ውጪ እንድመለከት እያደረገኝ ሲሆን የወሲብ ፍላጎት ከእኔ እንጂ ከእሷ መጥቶ አያውቅም፤ በእኔው ግፊት በወር አንዴ ወይንም ሁለቴ ግንኙነት ብንፈጽም ነው፡፡ በግልጽም ምንም አይነት ፍላጎት እንደሌላት ነግራኛለች፤ የሚገርመው ነገር እናቷም የተመሳሳይ ችግር ተጠቂ ነበሩ፡፡ ሁኔታው እጅግ እያስፈራኝ ስለሆነ እና ለትዳራችንም አደጋ ስለሆነ መፍትሄ ነው የምትሉትን ነገር ጠቁሙኝ፤ እኔም ምን ማድረግ እንዳለብኝ ምከሩኝ፡፡ ፋንታሁን ነኝ

ask your doctor የዶ/ር ዓብይ ዓይናለም ምላሽ፦ ውድ ጠያቂያችን ፋንታሁን በቅድሚያ ችግርህን ገልፀህ ከዘ-ሃበሻ ጋር ለመመካከር ስለወሰንክ እናመሰግናለን፡፡ በመቀጠል ወደ ጉዳይህ ስንገባ በትዳር አጋርህ ላይ የተፈጠረው የወሲብ ፍላጎት መቀነስ ብሎም መጥፋት እንዳስጨነቀህ እና እንዳሳሰበህ ምንም እንኳን እናንተ ብትዋደዱም በመሀከላችሁ የተፈጠረው ችግር ሊለያያችሁ እንደሚችል ያለህን ስጋትህን ገልፀሀል፡፡ ውድ ጠያቂያችን ፋንታሁን በቅድሚያ አንድ ነገር ተገንዘብ፡፡ ይህ አይነቱ ችግር የአንተ እና የባለቤትህ ችግር ብቻ ሳይሆን የበርካታ ባለትዳሮች ችግር መሆኑን፡፡ ሌላው በቅርቡ በእስራኤል ሀገር በኢየሩሳሌም ዩኒቨርሲቲ በተደረገ አንድ ጥናት ወሲብ የመፈፀም ፍላጎት ከሰው ወደ ሰው የተለያየ መሆኑን እና በተፈጥሮ አንዳንድ ሰዎች ከፍ ያለ ወሲባዊ ፍላጎት ሲኖራቸው ሌሎች ደግሞ አነስተኛ የሆነ ወሲባዊ ፍላጎትን ይዘው ይወለዳሉ፡፡ በዚሁ ጥናት ላይ በተደረገ ፆታዊ ንጽጽሮሽም ሴቶች ከወንዶች ያነሰ ወሲባዊ ፍላጎት እንዳላቸው ተደርሶበታል፡፡ ይሁን እንጂ የአንተ ባለቤት ላይ እንደሚታየው አይነት ዝቅተኛ የሆነ ወሲባዊ ፍላጎት (ሴክሽዋል ዲዛየር) በእንግሊዝኛ ሀይፓ አክቲቭ ሴክሽዋል ዲዛየር ዲስኦርደር በመባል የሚታወቅ ሲሆን ዋነኛ መገለጫውም ምንም አይነት አካላዊም ሆነ አዕምሮአዊ ችግር ሳይኖር ወሲባዊ ፍላጎትን ማጣት እና በወሲባዊ እንቅስቃሴ ምንም አይነት የደስታ ስሜት ያለመስማት ይልቁኑ፣ በተግባሩ የመረበሽ ስሜትን ማስተናገድ ነወ፡፡ ይህንን መሰል ስሜት በርካታ ሴቶች በተለያየ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የሚያስተናግዱት ሲሆን በአንዳንድ ሴቶች ላይ መጠኑም ሆነ የጊዜ ርዝማኔውም ከፍ ያለ ነው፡፡ ቀደም ባለው ጊዜ ይህ አይነቱ የወሲብ ፍላጎት መጥፋት እንደ ችግር አይቆጠርም ነበር፡፡ በጉዳዩ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የስነ ወሲብ ባለሞያዎቹ ዊልያም ማስተር እና ቨርጂኒያ ጆንሰን ጥናት እና ምርምር ካካሄዱ በኋላ ግን እንደ ችግር ትኩረት እያገኘ የመጣ፡፡ በተመሳሳይ ሄለን ሲንገር ካፕላን በተባለች የስነ ወሲብ ባለሞያ አማካኝነት በተደረገ ጥናት ወሲባዊ ፍላጎት (ሴክሽዋል ዲዛየር) በወሲብ ዑደት ውስጥ ወሲባዊ ፍላጎት (ሴክሽዋል ዲዛየር) በወሲብ ዑደት ውስጥ ከመነቃቃት፣ ከእርካታ እና ወደነበርንበት ቦታ ከመመለስ (Arousal, orgasm and resolution) በፊት የሚከሰት የዑደቱ የመጀመሪያው ክፍል መሆኑን ጠቅሳለች፡፡ ስለዚህ በውስጣችን የወሲባዊ ፍላጎት መፈጠር በወሲባዊ እንቅስቃሴ ዑደት ውስጥ የመጀመሪያው እና ወሳኙ ነገር ነው፡፡ ይሁን እንጂ እንደ አንተ ባለቤት ወሲባዊ ፍላጎት ከነጭራሹ ማጣት በእንግሊዝኛ ሀይፓ አክቲቭ ሴክሽዋል ዲዛየር ዲስኦርደር የሚባል ሲሆን፣ ዋና መገለጫውም ምንም አይነት አካላዊም ሆነ አዕምሮአዊ ችግር ሳይኖር ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ ወይንም መጥፋት ሲሆን፣ ይህን አይነት ስሜት የሚያስተናግዱ ሴቶች ወሲብ መፈፀምን ሲያስቡ እሱን ተከትሎ የሚመጣው ደስታ ሳይሆን የሚያስቡት የሚሰማቸውን ህመም እና የሚመጣባቸውን ጥሩ ያልሆነ ትውስታ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ሁልጊዜ የወሲብ ጥያቄ ሲቀርብላቸው የመከፋት፣ የመደበር እና የመነጫነጭ ስሜትን ያንፀባርቃሉ፡፡ በዊልያም ማስተር እና በቨርጂኒያ ጆንሰን አማካይነት የተደረገው ጥናት እንደሚጠቁመው የወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ ችግር ሶስት አይነቶች አለው፤ እነሱም፡-
- በህይወት ዘመን ውስጥ ዘላቂ እና አጠቃላይ የሆነ ወሲባዊ ፍላጎት ማጣት
ይህ አይነት ችግር ያለባት ሴት ዝቅተኛ ወይንም ምንም አይነት ወሲባዊ ፍላጎት የላትም ኖሯትም ላያውቅ ይችላል፡፡
- ከጊዜ በኋላ የተፈጠረ እና ቦታ ለይቶ የሚጠፋ ወሲባዊ ፍላጎት፣
ይህ አይነቱ የወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ ጤናማ የሚባል ወሲባዊ ባህሪ የነበራት ሴት ከጊዜ በኋላ ከትዳር አጋሯ ጋር ወሲብ የመፈፀም ፍላጎትን ታጣዋለች፡፡ ከሌላ ሰው ጋር ግን የመፈፀም ፍላጎት ሊኖራት ይችላል፡፡
- ከጊዜ በኋላ የተፈጠረ እና አጠቃላይ የሆነ ወሲባዊ ፍላጎት ማጣት፣
ይህ አይነቱ ወሲባዊ ፍላጎት የማጣት ችግር ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚፈጠር እና ቦታ እና ጊዜን ሳይለይ ሙሉ ለሙሉ ፍላጎት ማጣት ነው፡፡
ውድ ጠያቂያችን ፋንታሁን ከላይ ከተዘረዘሩት የወሲብ ፍላጎት መቀነስ አይነቶች በመነሳት ባለቤትህ በየትኛው ምድብ ውስጥ እንዳለች እወቅ፡፡ ሌላው ስለ ሴቶች ወሲባዊ ባህሪ ማወቅ ካለብን በርካታ ነገሮችን መካከል አንዱ እና ዋነኛው ነገር ሴቶች እንደ ወንዶች በፍጥነት ወሲባዊ ፍላጎታቸው አይነሳሳም፣ ሌላው ሴቶች ወሲባዊ እርካታን ማስተናገድ የሚጀምሩት በስጋዊ ግንኙነት ብቻ ሳይሆን ከዚያ በፊት በሚደረጉት ጨዋታዎች እና አካላዊ መቀራረቦች ጭምር ነው፡፡ ውድ ጠያቂያችን ፋንታሁን በቀጥታ ወደ አንተ ባለቤት ጉዳይ ስንመጣ በባለቤትህ ላይ የሚታየው የወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ በተለያዩ ምክንያቶች ሊከሰት ይችላል፡፡ እነዚህን ምክንያቶች በአራት ዋና ዋና ክፍል ማስቀመጥ እንችላለን፡፡
- ግለሰባዊ ችግር
- የመጣንበት ቤተሰብ ሁኔታ
- በጥንዶች መካከል ያለው የመቀራረብ ደረጃ
- የሌላ ጤና ችግር ተጽዕኖ
እነዚህን ዋና ዋና ምክንያቶች ሰፋ አድርጎ ለመመልከት ያህል፣ ግለሰባዊ ችግር በምንልበት ወቅት ከዚህ በፊት በነበረን ህይወት ከወሲብ መፈፀም ጋር በተገናኘ የሚፈጠር የፍርሃት ስሜት፣ በተለያየ ምክንያት የሚከሰት የድብት ስሜትት የትዳር ወይንም ወሲብን አስመልክቶ የሚኖር የተሳሳተ እምነት፣ በራስ ያለመተማመን እና ለራስ ዝቅተኛ የሆነ ግምት መስጠት፣ የስራ ጫና እና የሀሳብ ብዛት በራሱ ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስን ሊያስከትል ይችላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኃይል በተቀላቀለበት መንገድ የሚፈጠር ወሲባዊ ጥቃት እና ጥቃቱን ተከትሎ የሚፈጠር የስሜት ስብራትም ወሲብን ከዚያ መጥፎ አጋጣሚ ጋር በማስተሳሰር ስለወሲብ ጥሩ ያልሆነ ስሜትን ማዳበር ነው፡፡ ይህ ስሜት ደግሞ የወሲብ ፍላጎት መጥፋትን ሊያስከትል ይችላል፡፡
በተመሳሳይ የመጣንበት የቤተሰብ ይንም ያደግንበት ሁኔታም መሰል ችግርን ሊያስከትል ይችላል፡፡ በተለይ ያደግንበት ቤተሰብ ጥብቅ እና ሃይማኖታዊ ከነበረ እና ወሲብን እንደ ሐጢያት፣ እንደ እርከሰት እና አሳፋሪ እንደሆነ ነገር እንድንመለከት አድርገው ካሳደጉን ወሲብን የመጥላት እና ፍላጎት የማጣት ስሜት እንዲፈጠር ሊያደርገን ይችላል፡፡
በሌላ በኩል በጥንዶች መካከል ያለው የመቀራረብ ሁኔታም ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስን ሊያስከትል ይችላል፡፡ በጥንዶች መካከል ያለው መተሳሰብ፣ መከባበር እና መቀራረብ ከወሲብ የሚገኘውን የእርካታ ደረጃ ይወስነዋል፡፡ ለምሳሌ በጥንዶች መካከል ያለመከባበር እና የመናናቅ ስሜት ካለ፣ መተቻቸት እንዲሁም መከራከር እና እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ እና መሰል ጤናማ ያለሆኑ ግንኙነቶች ካሉ ፍቅርን የማሻከር ብሎም ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስን ከፍ ሲልም የማጥፋት አቅም አላቸው፡፡
ከላይ ከተጠቀሱት ምክንያቶች በተጨማሪ በውስጣችን ወሲባዊ መነቃቃት እንዲፈጠር ምክንያት የሚሆኑት ሆርሞኖች በተለያዩ የጤና ችግሮች የተነሳ ምርታቸው መቀነስ እንዲሁም ለተለያዩ ህመሞች ተብለው የሚወሰዱ መድሃኒቶች የጎንዮሽ ጉዳትም የወሲብ ፍላጎት የመቀነስ ችግርን ሊከስት ይችላል፡፡
ውድ ጠያቂያችን፡- ፋንታሁን የወሲብ ፍላጎት መቀነስ በሴቶች ላይ ብቻ ሳይሆን በወንዶችም ላይ አነስተኛ ይሁን እንጂ ይከሰታል፡፡ ከላይ የጠቀስናቸው አራት ዋና ዋና ምክንያቶች በተለይ በሴቶች ላይ የወሲባዊ ፍላጎት መቀነስን ሊያስከትሉ የሚችሉ ሲሆን፣ የፍላጎት መቀነሱ ወይንም መጥፋቱ ጊዜው አሊያ ዘላቂ ሊሆን የሚችል ሲሆን አንዲት ሴት ግን የዚህ ችግር ተጠቂ ነች ብሎ ለመደምደም የሚከተሉት ባህሪያት መስተዋል አለባቸው፡፡ የመጀመሪያው የወሲብ ፍላጎት መጥፋቱ ጊዜን እና ቦታን ሳይለይ ሁልጊዜ የሚከሰት ከሆነ፣ ሌላው ወሲብ ለመፈፀም ውስጣዊ የሆነ ፍላጎት ቢኖርም እንኳን ሰውነት እና ወሲባዊ አካላት ለግንኙነት ዝግጁ ያለመሆኑ ዋና መገለጫዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ምልክቶች በስፋት ከታዩ ያቺሴት የዚህ ችግር ተጠቂ ነች ማለት እንችላለን፡፡
ወደ መፍትሄው ስንመጣ ከላይ ለመጠቆም እንደተሞከረው ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ ወይንም መጥፋት በተለያዩ በርካታ ምክንያቶች የሚከሰት በመሆኑ የተነሳ እንደ መንስኤው ሁሉ መፍትሄውም የተለያየ ነው፡፡ ምን አልባትም መፍትሄው የህክምና እና የስነ ልቦና ድጋፍን ያጣመረ ስለሚሆን የችግሩ ባለቤትም ሆነ የትዳር አጋሯ ጥንካሬን እና ከችግሯ ለመውጣት ያላትን ቁርጠኝነት ይጠይቃል፡፡ ህክምናን መሰረት ያደረገው መፍትሄ ስንመጣ ለድብርት ማስለቀቂያ ተብለው የሚሰጡ አነቃቂ እንክብሎች አዕምሮንም ሆነ አካልን የማነቃቃት እና ዘና የማድረግ ባህሪ ስላላቸው ወሲባዊ ፍላጎትን ከፍ የማድረግ አቅምም አላቸው፡፡ ስለዚህ እነዚህን መሰል መድሃኒቶች የወሲብ ፍላጎት መቀነስ ችግር ሲከሰት የሚሰጡም ናቸው፡፡ እነዚህ መድሃኒቶች የጎንዮሽ ችግር ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ባለሞያዎችን ቀርቦ ማነጋገር የግድ ነው፡፡
ከዚህ ሌላ ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ ወይንም መጥፋት በስነ ልቦና ባለሞያ አማካኝነትም ሊደገፍ ይችላል፡፡ ምክንያቱም ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ አልፈለግም ከሚል እና ከመሰል ለራስ አነስተኛ ግምት ከመስጠት ጋር የሚገናኝ ችግርም ስለሆነ ለራስ የምንሰጠው ግምት እና ክብር ከፍ ባለ ቁጥር እየተስተካከለ ሊሄድ ይችላል፡፡ ስለዚህ የስነ ልቦና ባለሞያው ይህንን ሂደት ሊደግፍ ይችላል፡፡ ውድ ጠያቂያችን በጥንዶች መካከል ጤናማ ያልሆነ ግንኙነት ካለ ማለትም ያልተፈታ ቅራኔ፣ ግጭት ወይንም አለመግባባት ካለ በዚያ ባልተረጋጋ መንፈስ ውስጥ ሆነው ለግንኙነት መነሳሳት አስቸጋሪ ስለሚሆን የወሲባዊ ፍላጎ መጥፋት ይከሰታል፡፡ ስለዚህ በጥንዶች መካከል የተፈጠረን ቅራኔ ወይንም ግጭት ካለ በቶሎ መፍታት ይህንን ችግር ለመቅረፍ ወሳኝ ነው፡፡ በሌላ በኩል ከላይ ወሲባዊ ፍላጎ መቀነስን ሊያስከትሉ የሚችሉ ነገሮችን ስንዘረዝር ቀደም ባለው ህይወታችን ላይ የተፈጠረ እና ከወሲብ ጋር የተከሰተ መጥፎ አጋጣሚም የወሲብ ፍላጎት መቀነስን ስለሚያስከትል ስለአጋጣሚው በግልጽ በማውራት በዚያ አጋጣሚ የተፈጠረውን ፍርሃት እና የተሳሳተ እምነት ከውስጣችን እንዲወጣ ማድረግ አለብን፡፡ በግልፅ መነጋገር ሲባል ደግሞ በመወነጃጀል እና በጭቅጭቅ መንፈስ ሳይሆን በመረዳዳት እና ችግሩን ለመፍታት ቁርጠኝነት በማሳየት መሆን ይኖርበታል፡፡


ልጓሙን የበጠሰው የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የስድብ ፈረስ ዳኛቸው ቢያድግልኝ

$
0
0

በ ዳኛቸው ቢያድግልኝ

ፕሮፌሰሩ በጽሁፎቻቸው እንዲህ ብለውናል

“…በዓለም ሕዝቦች መሀከል ውድድር ቢደረግ ያለጥርጥር አበሻ አንደኛ ከሚወጣባቸው ነገሮች አንዱ ልመና ሳይሆን አይቀርም፤ ለአበሻ፣ ልመና የኑሮ ዘዴ ነው……” http://www.goolgule.com/abesha-and-begging-1/

“…አዳም አበሻ ሳይሆን አይቀርም፤ ሁሉንም ነገር ብላ ከተከለከለው በቀር ብሎ ያስቀመጠው ይመስላል፤ በላባችሁ ወዝ ብሉ ተብለው አዳምና ሔዋን መረገማቸውን አበሻ ገና አልሰማም፤ አበሻ የተፈጠረው ገነት ውስጥ ቁጭ ብለህ ያለውን ሁሉ ብላ በተባለበት ጊዜ ነው፤ እግዚአብሄር አበሻን ሁሉንም ብላ ሲለው ምናልባትም በጆሮው ጭራሽ አታስብ ብሎት ይሆናል …….” (ሰረዝ የተጨመረ)

እስከናካቴው “ሆድ” የሚባል ቃል ከአበሻ ቋንቋ ፈጽሞ ቢሰረዝ ቋንቋው ብቻ ሳይሆን አበሻም ጉድ ይፈላበታል። አዕምሮ ፣ ሕሊና የሚባሉትን ቃላት አበሻ አያውቃቸውም፤ ተግባራቸውንም ሁሉ ለሆድ ሰጥቶታል። (ሰረዝ የተጨመረ) http://www.zehabesha.com/amharic/archives/9015

 

ልጻፍ ልተው… ምናልባት… እንዲያው ምናልባት በዚሁ የሚያበቁ ከሆኑ አይቶ እንዳላየ ማለፍ ይሻል ይሆናል ስል ልጓሙን የበጠሰው የስድብ ፈረሳቸው በማንአለብኝነት ጋለበብን። ባእዳን አበሽ እያሉና እየሰደቡ ይገድሉናል። የራሳቸው ታሪክ በረሀብ ቸነፈርና ስደት የተሞላ እንዳልሆነ ሁሉ በመዝገበቃላታቸው ውስጥ ኢትዮጵያን የረሀብ ምልክት አድረገው የሚያዋርዱን በርካታዎች ናቸው። ፕሮፌሰሩ በአንድ ወቅት ሲሉ እንደሰማሁዋቸው ወያኔዎች ከዱር ወደከተማ ሲገቡ ህዝቡን ፈሪ ለማድረግና የሚያከብረው ምልክት ለማሳጣት በየቀዬው በህብረተሰቡ ዘንድ የሚከበሩትን እያፈላለጉ በአደባባይ ፂማቸውን ይዘው በመጎተት ያዋርዱዋቸው ነበር። ይህን መሰሉ የወያኔዎች ተግባር በሚያሳዝን ሁኔታ በፕሮፌሰሩም ላይ በተደጋጋሚ ደርሶባቸዋል። የወያኔዎች ኢትዮጵያዊነትንና ኢትዮጵያን የማዋረድ ዘመቻ ዛሬም እንደቀጠለ ነው። ታዲያ ይህ ባለበት ሁኔታ የእውቀት ጣርያ ላይ ደርሰዋል የሚባሉት አዛውንቱ ፕሮፌሰር መስፍንም በአሮጌና ያለአግባብ በተደረደረ ምሳሌ ይህን መከራ የበዛበትን ህዝባችንን በሚሸነቁጥ የጅምላ ስድብ መቀጥቀጣቸው ግር የሚያሰኝ ሆነብኝ። ይህ ወቅትና ሁኔታን ያላገናዘበ መፍትሄ የመጠቆም፣ የማስተማር አቅምም የሌለው ኢትዮጵያዊነትን የሚያዋርድ ጅምላ ስድብና ሽሙጥ በተከታታይ ሲወርድብን አይቶ እንዳላየ ማለፉ ክብራችንን ለማጉደፍና ለማዋረድ ኢትዮጵያችንን ለማንቋሸሽ ለሚተጉት ዱላ ማቀበል ይሆናል። እናም ይህ ጥያቄ ይከነክነኝ ገባ። እውን አበሻ ሥራ ጠል፣ ለማኝና ሆዳም ነውን? በምን ጥናት በማንስ ትንታኔ?

 
እድሜአቸውን ሙሉ ሀገራችንን አገልግለዋል ሲባል መስማቴ ብቻ ሳይሆን በባህላችን አዛውንት ይከበራልና ክብራቸውን የሚያጎድፍ ትችት ማቅረብ አልፈልግም። ቢሆንም ታድያ የሰሞኑ ማቆሚያ ያጣው የስድብ ጅራፍ ዘላቂ ጉዳቱ ከፍተኛ ነውና አክብሮቴን ሳላጎድል እባክዎን የስድብ ፈረስዎን ልጓም ያዝ አድርጉልን እላለሁ።
በሀገራችን አዋቂ ነን የሚሉ ሰዎች ከነሱ የተለየ ሃሳብ ይዞ የሚመጣን ተወያይቶ የተሻለውን ሃሳብ ከመደገፍ ይልቅ ለየት ያለ ሃሳብ ያቀረበውን አንገት የሚያስደፋ የስድብ ናዳ ማውረድ ይቀላቸዋል። ይህንን በመፍራት አዋቂዎቹ ግዙፍ ስህተት ሲፈጽሙ በዝምታ ማለፍ ለሌላ ስህተት በር መክፈት ይሆናል። አንዳንድ ሰዎች ደግሞ ጽሁፍን በይዞታው ሳይሆን በጸሃፊው ማንነት እየመዘኑ ጸሀፊው በግልጽ ያስቀመጠውን ሃሳብ ወደጎን ትተው ያልተባለውን መልካም ሃሳብ ፍለጋ እየማሰኑ የራሳቸውን ትርጓሜ ይሰጣሉ። ሰአሊ በስህተት የረጨውን ቀለም “አብስትራክት” ነው ብለው በምናባቸው ውብ ስዕል እንደሚሰሩት አይነት ከስድብ ጀርባ ሙገሳ መፈለጉ ከንቱ ነው።

 
የፕሮፌሰር ተከታታይ ጽሁፎች የተጻፉት ኢትዮጵያን በስፋት በማያውቅ ሰው፣ ሀሳብን ለህዝብ ለማቅረብ ምን አይነት ጥንቃቄ የተመላበት የምርምር ጥበብ አስፈላጊ እንደሆነ በማያውቅ ሰው ቢሆን፣ ሀሳብን የማስፈር ዓላማና ግብን መረዳት በማይችል የእውቀት አድማሱ ያልሰፋ፣ በሌሎች ሀገራት የሚኖሩ ሰዎችን አኗኗር በተመለከተ ምንም ግንዛቤ በሌለው ሰው ወይም እንዲያው ለፌዘኛ የመሸታ ቤት ቀልድ ሲባል ለተወሰኑ ታዳሚዎች የቀረበ ቢሆን ምንም ትኩረት መስጠት ባላስፈለገ ነበር። ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ግን አለምን ተዘዋውረው የጎበኙና ያልኖሩበትን ዘመንና ያልጎበኙትን አገር ህዝብ አኗኗር በምርምርና በንባብ ጠንቅቀው የተረዱ እድሜ የጠገቡ ምሁር ናቸውና በምንም ጥናታዊ መረጃ ባልተደገፈ መንገድ የአንድን ጥንታዊና ታሪካዊ ሀገር ሕዝብ በዚህ መልኩ ማሳነስና ከሌላ ፕላኔት የመጣ ሰንካላ ፍጡር ማስመሰል እድሜያቸውንና እውቀታቸውን አይመጥነውም። የአንድ ሀገር 90 ሚሊየን ሕዝብ በአንድ ቅንፍ ውስጥ “አበሻ” ብለው ከተው እንኳን የሰው ልጅ ቀርቶ ማንኛውም ማህበራዊ እንስሳ የሚያደርገውን ተሳስቦ፣ ተዛዝኖ፣ ተካፍሎ መኖርን በዚህ መልክ አሳንሶ ኢትዮጵያዊነትን ማዋረድ ታላቅ ስህተት ነው።

 

ኢትዮጵያዊነትን እያዋረዱ አገር አልባ ሊያደርጉን አዲስ ታሪክ ሊጽፉልን ያሰፈሰፉ ጠላቶች አራት ኪሎ በተቀመጡበት ሰዓት፤ ከልመና ግርድና ይሻላል ብለው የፕሮፌሰሩ የልጅ ልጆች በመላው አለም ተበትነው ለራሳቸውና ለቤተሰባቸው ቢያልፍልን ብለው በሰው ሀገር እየተደፈሩ፣ እየተዋረዱ በሚዳክሩበት በዚህ ዘመን፣ በርካታ እናቶች አራስ ልጆቻቸውን ታቅፈው ትንሽ ሳንቲም ለማግኘት በየመንገዱ ዳር ጥቂት የተቀቀለ ድንችና ንፍሮ ለመሸጥ ጸሀይና ብርድ ሲፈራረቅባቸው ውሎ በሚመሽበት ዘመን፣ ደካማ እናቶች ወገባቸው እስኪጎብጥ ቅጠልና ጭራጭሮ ተሸክመው የእለት ጉርሳቸውን በሚያገኙበት ሀገር፣ ተራራ የሚያክል ሸቀጥ በጭንቅላታቸው ተሸክመው የሚሮጡ ወገኖች በሚርመሰመሱበት ሀገር፣ ህጻን አዛውንቱ ትንሽ ባገኝ ብሎ ሊስትሮና ማስቲካ ነጋዴ በሆነበት ሀገር ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያውያን ሥራ-ጠል ሆዳምና ለማኝ መሆናችንን አስረግጠው ሲነግሩን መስማት እጅጉን ያማል።
 

ሀገር በሞታቸው ያቆዩልን ተዋርደው አጽማቸው ከመቃብር ሀውልታቸው ከቆመበት እየፈረሰ ባለበት፣ የኢትዮጵያን ገጽታ ማቆሸሽ የመንግስት ፖሊሲ በሆነበትና ግፈኞችና ጎጠኞች ሰው በሀገሩ ሰርቶ ሰው መሆን እንዳይችል በየማዕዘናቱ እየበተኑት ባሉበት የመከራ ጊዜ የኛው የተማሩ አዛውንት ዋናው ተሳዳቢ መሆናቸው ያሳዝናል። አብረን ስለበላን ሆዳም፣ ተቸግሬአለሁ ብሎ ድጋፍ ለጠየቀ ወገን ስለለገስን ኅሊና ቢሶች አሉን። ሰውን ከመዝረፍ መለመንን ስለመረጠ ፈሪና ጅል፣ ስላመነ ሞኝና ተላላ አድርጎ መመልከት ነውር ነው። ይህ መተዛዘንና ተካፍሎ መብላት ቀለም ያልቆጠረው ኢትዮጵያዊ ያቆመውን መሰረትና ያቆየውን ባህላዊ እሴት ልናከብረውና ልንከባከበው ይገባል። በተከታታይ በፕሮፌሰሩ የተጻፉት ጽሁፎች የሚደመድሙት አበሻ ስራ ጠል መሆኑን፣ ሆዳምነቱንና፣ ለማኝነቱን ነው። በሚቀጥለው ጽሁፋቸው ደግሞ ሌላም ሊያስከብሩን የሚገባቸውን ባህሪያችንን ልናፍርባቸው የሚገቡ አጉል ገጽታዎች አድርገው ይጽፉልን ይሆናል። ይህ ወይ እራስን ከፍ ከፍ ለማድረግ ሌላውን ዝቅ ዝቅ ማድረግ በመፈለግ አለዚያም ተስፋ የቆረጠ ሰው አገርን በጅምላው ሊያስነውር የሚያደርገው ድርጊት ይመስላል።
 

ለመሆኑ ፕሮፌሰሩ ሆድ መውደድን እንዴት ይገልጹታል? ምግብ መውደድ፣ መውደድ ብቻ አይደለም አጣፍጦና አስውቦ መብላት አንደምንስ ያስወቅሳል? በውጪው አለም የምግብ ስራ ጥበብ ምንኛ የተከበረ ሙያ መሆኑን፣ ቴሌቪዥኑ በሙሉ በምግብ ስራ ፕሮግራም መጨናነቁንና የምግብ ስራ ጥበብ መጻህፍት ጸሀፊዎች ምንኛ የተከበሩ መሆናቸውን እንዴት ዘነጉት? ምግብ እኮ የህልውና መሰረት ነው በአካል ለመዳበር፣ አእምሮን ለማጎልበት፣ የማስታወስና የማሰብ አቅምን ከፍ ለማድረግ የታመቀውን የተፈጥሮ አቅም ለማውጣት የሚያግዝ ነው። በጣም የሚገርመው ደግሞ ቢወደውም ጥቅሙን ቢረዳውም እንኳ አልሚ ምግብ አግኝቶ ሳይሆን በተገኘው ምግብ ሆዱን ሞልቶ የሚያድር እንኳን በሌለበት ሀገር ውስጥ ለሚገኝ ሕዝብ በረሀቡ ላይ ሆዳም የሚል የስድብ ምርቃት ማከሉ አሳዛኝ ነገር ነው። ምክርም ይሁን ግልጽ ዓላማ የሌላቸው ጽሁፎች መጻፉ ግቡ ኢትዮጵያን ለሚያዋርዱት ‘ምሁራዊ’ ድጋፍ መስጠት ብቻ ይመስለኛል።

 
በምግብ አብዝቶ መብላትና ሲያመነዥጉ በመዋል የሚታወቁት የሌሎች አገሮች ዜጎች ናቸው። ይህንን የማያውቅ ከመንደሩ አለፍ ብሎ የማየት እድል ያልገጠመው ሰው እንጂ እንደ ፕሮፌሰር አውሮፓ ኤዥያና ሰሜን አሜሪካን ያሰሰ ሊሆን አይችልም። ለዚያውም ባንድ ወገን ሆዳምና አይነቱና ብዛቱ ወደር የማይገኝለት ምግብ ስለመብላቱ የሚነገርለት ሕዝብ በሌላው የፕሮፌሰሩ ፅሁፍ ለማኝነቱንና አምላክ ደድብ ያለው ሥራ-ጠልነቱ ይበሰርለታል። አንዱን ፅሁፋቸውን ከሌላኛው ማገናኛ ድልድዩ ምን ይሆን ያሰኛል። ለማኝ እኮ አጣጥሞና አማርጦ ለመብላት ያልታደለ ምርጫ አጥ ነው። ሥራ ጠልቶና ለምኖ አማርጦ መብላት ከተቻለማ ኢትዮጵያችን መና ከሰማይ የሚዘንብባት ሁናለች ማለት ነው።

 
ኢትዮጵያዊም ሆነ ሌላው በገበታ ዙሪያ የሚሰባሰበው ለመብላት ምክንያት በመፈለግ አይደለም፤ ምግቡ የመገናኛው ማጣፈጫ እንጂ። ሰርግም ሆነ መልስ፣ ልደትም ሆነ ተዝካር፣ ፋሲካም ሆነ እንቁጣጣሽ በጋራ ገበታ መቀመጥ መሰረታዊ ምክንያቶቹ ማህበራዊ ግንኙነቶች ናቸው። የሰው ልጅ ማህበራዊ እንስሳ ነው። አብሮነቱን ካላዳበረ ተነጣጥሎ ይሞታልና የትኛውም ማህበረሰብ በየትኛውም የዓለም ጫፍ ቢኖር በራሱ መንገድ ይሰባሰባል። አብሮ ያድናል፣ ተጋግዞ ያርሳል፣ ፈረቃ ገብቶ ያመርታል። ያንን ውበት ለመስጠትና አብሮነቱን ለማሳመር ደግሞ በጋራ ገበታ ይቁዋደሳል። ታዲያ ለምንድን ነው ኢትዮጵያውያን አብረው መብላታቸው ልዩ እንከን ተደርጎ የሚቀርበው? እንዲያውም ኢትዮጵያውያንን ሰብስቦ የያዘው ጠንካራ ድር ቢኖር እንዲህ ያለው በደስታና በሀዘን አብሮ መሆኑ ነው። አብሮ ያቆመን ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው ባህላዊ እሴት እንደ ሁዋላ ቀርነትና ሆዳምነት ሲቆጠር ስቆ ማለፉ የሚያስከትለውን እራስን የማዋረድን ጣጣ ልብ ያለማለት ነው። ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የቆዩ በአብዛኛው ከሀይማኖት ጋር የተገናኙ አሰባሳቢና አገናኝ በዐላት አሏቸው። በለጸጉ የሚባሉት አገሮች ደግሞ ከሀይማኖታዊ በአላት በተጨማሪ ለንግድ የሚመቹ አዳዲስ በዐላት እየፈጠሩ አብሮነታቸውን የሚያጠናክሩበትን መንገድ ፈጥረዋል። የእናት ቀን፣ የአባት ቀን፣ የፍቅር ቀን፣ የምስጋና ቀን እያሉ አብረው ይበላሉ ይጠጣሉ። ስለዚህም ኢትዮጵያውያንን አብረው በመብላታቸው ሆዳም የሚላቸው በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ትንሽም ቢሆን ጥናት ያላደረገ ብቻ ነው።

 

ከዚህ ቀደም እንደ ጻፍኩት ኢትዮጵያውያንን ‘አበሻ’ ባልል እመርጣለሁ ምክንያቱም ኢትዮጵያ የሚለውን ስም ለማሳነስ በርካቶች አበሻ የሚል ስያሜ ላይ በመንጠልጠል መጥፎና ደካማ የሆነውን ነገር ሲያጎሉ ማየት እየበዛ ነው። ‘አበሽ’ የሚለውን የንቀት መሰል አጠራር የሚጠቀሙትም እነማን እንደሆኑ እናውቃለንና ኢትዮጵያ እያልኩ እቀጥላለሁ። እናም ክቡር ፕሮፌሰር የአለም ሕዝብ ከእንቅልፉ ተነስቶ ማዛጋት ሲጀምር ነቃ የሚያደርገውን ቡና…. ፓስታና ማኮሮኒ እያማረጠ የሚበላበትን ስንዴ…. ‘ግሉቲን’ ሆዱን እየነፋው ፊቱን እያዠጎረጎረ የሚያስቸግረውን ሕዝብ ጤናማ የሆነ እሹኝ ፈትጉኝ የማይለውን ጤፍ ጠገብ ሲል ደግሞ የበላውን የሚያወራርድበትን ጥሙን የሚያስታግስበትን ገብስ ለአለም ያበረከተው “ሰነፍ፣ ሆዳምና ለማኝ” እየተባለ የሚዘለፈው የኢትዮጵያ ገበሬ ነው። የሀገሬ ገበሬ ጀምበር ወጥታ እስክትጠልቅ ድረስ የሚተጋ ጠዋት ያሟሸውን አፉን ማታ ባገኛት እፍኝ እህል እየዘጋ የሚኖር ነው። ይህ ደግሞ ከሰማንያ በመቶ በላይ ኢትዮጵያውያንን ይወክላል። ይህ ወገንዎ ክብር እንጂ ስድብ፣ ሙገሳ እንጂ ውርደት አይገባውም። በምንም መልኩ ኢትዮጵያውያንን እርሶንም ጨምሮ እግዜር በጆሮአችንን አታስቡ ብሎ መርጦ አላደደበንም። ያንን ስድብ ተቀብለው የሚኖሩ ደደቦች ካሉ ምህረቱን ያውርድላቸው። ሀገራችንን ለማጥፋት የሚያዋርዱን በቂ ጠላቶች አሉንና እራሳችንን በማዋረድ ለጠላት ስራውን አናቅልለት።

 
ኢትዮጵያውያንን ከሀገራቸው ውጪ የሚያሳዩትን የስራ ፍላጎትና መነሳሳት ለመመልከት እድል ላገኙ ሁሉ ኢትዮጵያውያን ሀገሬውንም ሆነ ሌሎቹን መጤዎች በልጠው ሲተጉና ውጤትም ሲያመጡ እንጂ ሰነፍ በመሆን ከሌላው አንሰው አያዩም። ስለዚህ በጅምላ ኢትዮጵያውያንን ስራጠል ሰነፍ አድርጎ መኮነኑ ውሃ አያነሳም። ኢትዮጵያውያን ስራጠል ከሆኑ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች ስለምን ወደ አረብ አገር ሊሄዱ ቻሉ? ለልመና ነበር? ለመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተሰደዱባቸው ሀገራት በአውሮፓና አሜሪካ በአፍሪካ ሀገራትም እንኳን የሚታወቁት በስራ አይደለምን? ባዶ እጃቸውን ከሀገር ወጥተው አዲስ ሀገር ውስጥ ኑሮ መስርተው ከብረው ለመኖር የቻሉት በአስማት ነውን? ስለዚህ ፕሮፌሰሩ እነዚህ በአንዲት ጀንበር ዘርፈው የከበሩ ነጣቂዎችን መንግስት ብለው መንግስት አንደተቀበለው ቻይና እንዳረጋገጠው ብለው ስንፍናችንን ሲደመድሙ የፌዘኛ እንጂ ምሁራዊ ትችት አይመስልም። አንድን በይሉኝታና በፈሪሃ እግዚአብሄር (አምላክ) የሚኖርን ሕዝብ አዕምሮና ሕሊና ቢስ የሚል ሰው እውን ሕሊናና አእምሮ አለው ብሎ መገመትስ ይቻላልን?
ኢትዮጵያውያንስ እንዴት ሁኖ ነው በሆዳቸው ነው የሚታወቁት የተባለው? ኢትዮጵያውያን ተጋብዘው ድግስ እንኳን ሲሄዱ “ቤታቸው ምግብ የለም እንዴ” ላለመባል እቤታቸው በልተው የሚሄዱ ናቸው። ነፃ ምግብ አለ ሲባሉ ለሳምንት የሚበቃ ቀለብ በሆዳቸው ለመጫን የሚዳዳቸው ሌሎች አንጂ ኢትዮጵያውያን አይደሉም። ኢትዮጵያዊውማ ከሆዴ ይልቅ ክብሬ በማለት እርቦትም አሁን በላሁ ነው የሚለው።

 
ሰዎች ይህንን ስራ ከምሰራ ለምኜ እበላለሁ የሚሉበት ዘመንም ከነበረ በትንሹ ግማሽ ምዕተ አመትን አሳልፏል። ይህም ክስ እውነት እንኩዋን ቢሆን ኢትዮጵያውያንን ለይቶ ከንቱና ርካሽ የሚያደርግበት ምንም ሚዛን የለም። በየትኛውም የአለም ክፍል ቢሆን በአንድ ወቅት የተናቀ ስራ ነበር። ዛሬም ቢሆን ይህን ከምሰራ ዌልፌር ምን አለኝ ብሎ እጁን አጣጥፎ የሚቀመጥ ስንት ፈረንጅ በየሀገሩ አለ። ሌላም አንድ እውነት አለ፣ ሰዎች ከልምዳቸው ውጪ የሚመጣን ነገር የመቀበል ፍላጎታቸው ውሱን ነው። ለምሳሌ ከብት አርቢዎች እርሻን በንቀት ይመለከታሉ። አንዳንድ ከብት አርቢዎች ለምን እነደዚህ ያለ ስራ አትሰሩም የሚባል ከአካባቢው ሁኔታ ጋር የተያያዘ ጥያቄ ሲቀርብላቸው የኛ ዘሮች ይህንን አይሰሩም ይህን የሚሰሩት ሌሎች ናቸው ይላሉ። አንጥረኞች፣ አዝማሪዎች፣ ነጋዴዎች ሁሉም የለመደውን ስራ አጥብቆ መያዝ የኢትዮጵያውያን ብቻ ባህሪይ አይደለም። እንዲያም ሆኖ ኢንጅነሮች፣ የሙዚቃ ጠበብቶች፣ ዶክተሮች የመንግስት ተጡዋሪ ላለመሆንና ለቤተሰባቸው የተሻለ ህይወት ለመስጠት ስራ ሳይንቁ ከጠዋት እስከማታ መኪና በመጠበቅ፣ ታክሲ በመንዳት፣ ዘበኛ በመሆን፣ ጽዳት ሰራተኛ በመሆን ይዳክራሉ። እንዴት ነው ይህን ህዝብ ስራጠል አድርጎ መኮነን የተቻለው?

 
በሀገራችን ያለጥናትና በቂ መረጃ በምሁሩ ምክር የሰው ንብረት መውረስና ማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ጥፋት በስመ ሶሻሊዝም በተፈጸመበት ጊዜ የተመለከትነው አንድ እውነት አለ። ሁለት ስራ መስራት አድሃሪነት ነበር ገንዘብ መያዝና ፈጠራ ወንጀል ነበር። ሶሻሊዝምን ያመጣውና መስራትንና መክበርን ወንጀል ያደረገው ተማርኩ ያለው ወገን የመረጠው የሶሻሊዝም መንገድ ነበር። እንዲያም ሆኖ በአዋጅ ሰዎች ድህነትን እንዲቀበሉ በተደረገበት ጊዜ እንደ አቅምቲ ከበርቴ ተብለው ሀብት ንብረታቸው እየተዘረፈ ሰዎች ወደ እስርቤት በተጋዙበት ጊዜ አዲስ አበባ የተከፈቱ ምግብ ቤቶች (ኢድዩ ቤቶች)፣ ባልትና ቤቶች ሁሉ ሕዝባችን ችግሩን ለማሸነፍ ምን ያህል የሚፍጨረጨር እንደነበረ የሚያስመሰክር ታሪካዊ ወቅት ነበር። እነዚያ “እመቤቶችና ወይዛዝርቶች” ሆቴል ቤት ከፍቼ ለማንም ከማስተናግድ ልመና እመርጣለሁ አላሉም።

 
ኢትዮጵያውያኖች ለማኞች መሆናችንን ፕሮፌሰር በተለያየ ምሳሌም አስቀምጠዋል። መንግስትን መጠየቅን፣ ሰውን መማለድን (ድርድርን)፣ ትህትናንና ሰላማዊነትን ፕሮፌሰር በልመናነት መድበውታል። እውነታው ግን እነኚህ ባህሪያት አስተዋይነትንና ህግ አክባሪነትን ነው የሚያመለክቱት። ሁሉንም በጉልበት የሚያስፈጽም ማህበረሰብ በሰላም መኖርም አይችልም። በርካታ ታጋዮች የኔ መንገድ ብቻ ነው ትክክል በማለት የተለየ አመለካከት ባሳየው ላይ ተከታታይ በደልን በመፈጸማቸው ሰዉ ክፉኛ እንዲሸማቀቅ ተደርጎአል። ነገርግን ሕዝቡ የለማኝ ባህሪ ተጠናውቶታል ብሎ መደምደም ከባድ ስህተት ነው። ፕሮፌሰር ደግሞ ሰላማዊ ትግል ብቻ የሚሉ እንደመሆናቸው መጠን ዘራፍ ብሎ ለዱላ ከመጋበዝ ይልቅ መንግስትን በጥሞና መማለድን የሚደግፉ ኢንጂ እንዴት የሚኮንኑ ሊሆኑ ይቻላቸዋል?

 

የመጽዋችና የተመጽዋች ግንኙነት ያለው ደግሞ በኢትዮጵያ ብቻ አይደለም። ምክንያቱም ያለውና የሌለው በየሀገሩ ነው ያለው። ያለው ደግሞ ለተቸገረው መቸርን የማያውቅ ከሆነ በሰላም ወጥቶ መግባትም አይቻልም። ከመለመን ይልቅ በጉልበት ቀምተው የሚወስዱ ነጣቂዎች የበረከቱበት ሀገር ይሻላል የምንል ካለን የማሰብ አቅማችን ተናግቶአል ማለት ነው። ኢትዮጵያውያን ካላቸው ላይ ቀንሰው ለሌላው መስጠታቸው የስነምግባርና የሞራል ባለጸጋ መሆናቸውን ያመለክታል እንጂ ልመናን የሚያበረታቱ ሰነፍ ማምረቻዎች አያሰኛቸውም። ጧሪ ያጡ አዛውንቶች፣ የአካል ጉዳተኞችና ህመምተኞች በመሆናቸው ስራ ማግኘት የማይችሉና ጤነኛም ሆነው ስራ ማግኘት ያልቻሉ መለመን ሊገደዱ ይችላሉ። ይህ ሰነፍ አያስብላቸውም። ባደጉት ሀገራትም የ ‘ዌልፌር/ድጎማ’ አሰራር አላቸውና ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የተለያዩ እርዳታዎችን ይለግሳሉ። ይህ መንግስታዊ ድጋፍ በሌለባት ኢትዮጵያ ወገን ወገኑን መርዳቱ አስፈላጊና የሚደነቅ እንጂ የሚያስወቅስ አይደለም። ኢትዮጵያውያን ይህንን የመረዳዳት ባህል ባያሳድጉ ኖሮ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት በተበተነ ጊዜ መሳርያውን ተሸክሞ ሰለ እግዚአብሄር ውሀ ስጡኝ ብሎ ባልጠየቀ ነበር። ተደራጅቶ መዝረፍ ሲችል ወርቅ ቤት ተደግፎ የሚለምን በዲሲፕሊን የታነጸ ጦር ኢትዮጵያ ብቻ በመኖሩ ጨዋና ህግ አክባሪ ያደረገንን ባህል ልናመሰግን ይገባል። ከዚህም ባሻገር ‘ልመና’ የሌለበት አገር የለም። አሜሪካም ሆነ አውሮፓ ወይም ኤዥያ በውበቱ ከሚያፈዝ ህንጻ ስር ቆቡን ዘርግቶም የሚለምን ሆነ ፕሮፌሰር እንደጠቅሱት የድሬዳዋ ለማኝ ብር ስጠኝ እያለ እንደማዘዝ የሚያደርገው ለማኝ ሞልቶዋል።

 
ልመናና ጸሎት ተመሳሳይ ትርጉም ከተሰጣቸው ደግሞ ሁሉም አገሮች ውስጥ ጸሎት አለና ልመናው አለምን አስጨንቆአል ማለት ነው። ድርድርም ልመና ከተባለ በትህትና የቀረቡ ጥያቄዎች ሁሉ ልመና ይደረጋሉና ጨዋነት እንደክፉ ባህሪ ሊታይ ነው ማለት ነው። ላሊበላነትም የልመና መስክ ሆኖ ተተችቷል። ነገር ግን ዘፋኝ ሲዲ አሳትሞ ለገበያ ሲያቀርብ ለማኝ አንለውም። አዝማሪዎችና ላሊበላዎች ደግሞ ዛሬ ላለው ኪነታዊ ጥበብ መሰረቶች ናቸው። ስለምን የቀድሞውን ነገር ሁዋላ ቀርና እርባና ቢስ እንደምናደርግ አይገባኝም።
የቆሎ ተማሪ በልመና ስለተለከፈ አይደለም የሚቀፍፈው። የሀገሬ ባላገርም የትምህርትን አስፈላገነት ስለተረዳ ካለችው ቆንጥሮ ያካፍላቸዋል። ፕሮፌሰርም ሲማሩ የተሰጣቸው መማርያ፣ የጠጡት ወተትና ልብሳቸውን ያጠቡበት ሳሙና እንደ ቆሎ ተማሪዎች ሰለ ማርያም ብለው ቆዳ ለብሰው ቀፈፋ ባይዞሩም ያው ከንጉሱና ከህዝቡ ቀፈፋ ነበር። እኛ ካልቻልንበት ያልቻልነውን በመጠቆም ማሻሻል እንጂ ያለፈው ትውልድ በቻለውና ባወቀበት መንገድ ሰርቶ ያቆመልንን አገር ማዋረድ ወንጀል ነው።

 
ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የቆመችው ባሉን ማህበራዊና ባህላዊ እሴቶቻችን ነው። የድሮውን አሳድጎ ዘመናዊ ማድረግ ወይም የተኮረጀውን ከሀገር አስማምቶ ጥቅም ላይ ማዋል ስላቃተን የነበረውን ስንወነጅል ልንኖር አይገባም። አገርን በጅምላ ስንወነጅል ራሳችን የምናበረክተውን እንገምግም። ራስን እያዋረዱ ክብር መሻት ሞኝነት ነው። ከልመና ለመውጣትና ገበና ለመሸፈን አስፈላጊ የሆኑ ተቋማት እንዲፈጠሩ ማበረታት ያሉትንም ማጠናከር እንጂ ወገን በሀዘኔታ ካለችው ላይ ስለሰጠ የተቸገረም ስለለመነ ማውገዙና በሽሙጥ መውገር ምን ይረባናል? ማንም በእርግጠኛነት ሊናገር የሚችለው ኢትዮጵያውያን ለማኝ፣ ሆዳምና ሥራ-ጠል ሳይሆኑ ዘመናትን የሚሻገር ባህልን ያሳደጉ ሲቸገሩ ተረዳድተው ሲመቻቸው አብረው ተደስተው የሚያኖራቸውን ባህል ያቆዩ ታታሪ ሰራተኞችና የሚረዳዱ መሆናቸውን ነው። የእውቀት መነጽራችን ይህንን ላላስመለከተን መቃወምና መንቀፍ ብቻ የእውቀት ምልክት የሚመስለን ህዝብን ከመስደቡ ብንታቀብና የማስተዋል አቅማችንን ብናዳብረው ይበጃል።

 
ሀገር አዋራጅ መሰረተቢስና ውልየለሽ ጅምላ ስድብን እውነት ነው ብሎ መቀበል ተቀብሎም ስድቡ ይገባናል በማለት እየተቀባበሉ መሰዳደብ ትክክል አይደለም። ስለዚህም በተከበሩ ፕሮፌሰር ስለተጻፈ ብቻ እንደታላቅ ግኝት በየሚዲያው ማሰራጨቱም “ሞኝን አንዴ ስደበው እራሱን ሲሰድብ ይኖራል” የሚለውን ብሂል በተግባር ማዋል ይሆናል። ኢትዮጵያንና በልጆቿ እየተሸረሸረ ያለውን ኢትዮጵያዊነትን እናድን ዘንድ እንትጋ።

 
comment_stage_5biyadegelgne@hotmail.com

 

 

እኔ ጃዋርን ብሆን ኖሮ ከዓለማየሁ መሀመድ(2)

$
0
0

ከዓለማየሁ መሀመድ(2)

በትላንቱ ጽሁፌ ጃዋርና ህወሀት የፈጸሙትን ለጊዜው መረጃው ብቻ ስላለኝ ያጋብቻ ጉዳይ አንስቼ በቀጠሮ ነበር የተለያየነው። ማስረጃው በቅርቡ እጄ እንደገባ ሰማንያ ተፈራርመው የሰሞኑን የፌስቡክ ግርግር እንዴት እንደገቡ ይፋ አደርጋለሁ። እስከዚያው ታገሰኙ።

ለአሁን ጃዋርን ብሆን አማረኝ

አዎ! ጃዋርን ብሆን ይሄን ጊዜ እነዚህን ነገሮች አደርጋለሁ

1. የኬንያና የህወሀት መንግስታት ተስማምተው የኦሮሞ ልጆችን እያደኑ ነው። ሰሞኑን ከወደ ኬኒያ እንደሚሰማው ከ 500 በላይ የወያኔን መንግስት ሸሽተው ኬኒያ የተጠለሉ ኦሮሞዎችን ኬኒያ አሳልፋ እየሰጠች ነው። በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ ስም ኦሮሞች ተለቅመው ለወያኔ መንግስት እየተሰጡ ነው። ይህ ዘመቻ አሁንም ቀጥሏል። እናም እኔ ጃዋርን ብሆን ኬኒያ እያደረገች ያለችው ድርጊት ዓለም ዓቀፉን የስደተኞች መርህ የሚጣረስ በመሆኑ ለመንግስታቱ ድርጅት፡ ለዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት፡ ለኬኒያ ፓርላማ እና ለሌሎች ድርጅቶችና መንግስታት አቤቱታ እንዲቀርብ አስተባብራለሁ። ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ ባለመሆኑ ያለኝን ማህበራዊ ቦታና ተቀባይነት ተጠቅሜ፡ ሰፊ የቅስቀሳ ስራ በማከናወን ኬኒያ ላይ ጫና እንዲፈጠር አደርጋለሁ።

2. በምስራቅ ሀረርጌ ከሶማሌ ክልል ድንበርተኛ በሆኑ ወረዳዎች ላለፉት ሶስት ዓመታት በልዩ የሶማሌ ክልል ታጣቂዎች እየተፈጸመ ያለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሰሞኑን ተባብሶ መቀጠሉ እየተነገረ ነው። የሶማሌ ልዩ ሃይሎች የኦሮሞ ሴቶች እየደፈሩ፡ናቸው። ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በተለያዩ አጎራባች አከባቢዎች የተሰደዱት ወገኖች ቁጥር ከፍተኛ ነው። የሚበሉት ያጡ ህጻናት እየረገፉ ናቸው። እናም እኔ ጃዋርን ብሆን ተመሳሳይ የቅስቀሳ ዘመቻ በመክፈት ጉዳዩ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ሰሚ እንዲያገኝና ወገኖቼ ከስቃይ እንዲድኑ የሚቻለኝን አደርጋለሁ። የገቢ ማሰባሰቢያ መድረኮች እንዲዘጋጅ እየቀሰቀስኩ ገንዘብ አሰባስቤ ለእነዚያ እየረገፉ ላሉት ህጻናት፡ መሄጃ መድረሻ ላጡት ወገኖቼ እደርስላቸው ነበር።

3. የወያኔ እስር ቤቶች በኦሮሞዎች ተጥለቅልቋል። በቅርቡ ኢንጅነር ተስፋሁንን ጨምሮ በርካታ ኦሮሞዎች በወያኔ የጭካኔ ተግባር በእስር ቤት እያሉ ህይወታቸውን አጥተዋል። ከሰሞኑ ሁለቱ የኦሮሞ መብት ታጋዮች አቶ በቀለ ገርባና አቶ ኦልባና ሌሊሳ በአንድ ዓይነት ህመም እየተሰቃዩ ነው። ህክምና ተነፍገው በከፍተኛ ስቃይ ላይ እንዳሉ ተሰምቷል። እናም እኔ ጃዋርን ብሆን ለእነ አምንስቲ ኢንተርናሽናል፡ ሂውማን ራይትስ ዎች እና ተጽእኖ ለሚፈጥሩ አካላት ጉዳዩን በማሳወቅ እስረኞቹን ከሞት እታደጋለሁ። ገንዘብ እንዲሰባሰብ በማድረግ ለእስረኞቹ ቤተሰቦች እርዳታ እንዲደረግ እቀሰቅሳለሁ።

ሌላም…. ሌላም…..

ግን ጃዋርን አይደለሁም። ባለኝ አቅም ጥረት እያደረኩ መሆኔን ግን መግለጽ እፈልጋለሁ። ጃዋር ካለው ማህበረሰባዊ ተቀባይነት አንጻር ከእኔ የተሻለ ውጤት ሊያስመዘግብ ይችላል ከሚል መነሻነት ነው ጃዋርን መሆን ያማረኝ።

ጃዋር ጆሮው ላይ የሚያቃጭለው የሙታን ድምጽ ነው። በዓይነ ህሊናው የሚሽከረከረው የሙት መንፈስ ነው። እየተላፋ ያለው ከማይጨበጥ ከማይዳሰሰው ጋር ነው። በህይወት ስላሉት ከንፈር እንኳን መምጠጪያ ጊዜ አላገኘም። ጠዋት ተነስቶ እስኪመሽ በኮምፒውተሩ ቂጥ ስር ተወሽቆ ኦሮሞ ፈርስት እያለ ማላዘኑ ተመችቶታል። የኬኒያዎቹ ኦሮሞዎችን ስቃይ የሚሰማበት ጆሮ የለውም። ለምስራቅ ሀረርጌዎቹ ህጻናት ሲቃ ጊዜም ሊሰጥ አልፈቀደም። በየእስር ቤቱ ለሚሰቃዩ የኦሮሞ ልጆች የሚያዝን ልቦና አልሰጠውም። ጸሀይ ወጥታ እስክትጠልቅ ከታሪክ ተራራ ጋር ይላፋል። ይቸከችካል። መሰሎቹ ጃስ ሲሉት ደስ ይለውና አሁንም ይቸከችካል። ሙቀቱ ተመችቶታል። ጭብጨባው ልቡን ላይ የትዕቢት ተራራ ቆልሎለታል። ድሮውንስ የኦሮሞ ህዝብ ስቃይ ለሱ የግል ዝና መሸመቺያ እንጂ መቼ መቆርቆር ከአጠገቡ ደርሳ?

ለማንኛውም በቅርቡ የጃዋርንና የህወሃትን ጋብቻ የተመለከተውን ማስረጃ ይዤ እመለሳለሁ። ለዘነጋችሁ; ጃዋር የወያኔ አሻንጉሊት የሆነው ኦህዴድ ልጅ ነው። ውለታ አለበት። ለአቅመ ፖለቲካ እንዲደርስ ያበቃውን ኦህዴድን(ህወሀትን) ቢረሳ አምላክም ደስ አይለውም። ወደፊት የማካፍላችሁ ዕውነትም ከዚሁ ጋር የተያያዘ ነው።

በመጨረሻም ለፈርስቶች መልካም የጩኧት ጊዜ። ሙቀቱ ሲለቃችሁ እንገናኝ።

comment pic

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ ተከፈተ::

$
0
0
Andinet Party

ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ ‹‹የአባይ ግድብ በየትኛውም መመዘኛ የአንድ ግለሰብና ፓርቲ ራዕይ መሆን አይችልም፡፡ኢህአዴግ ራሱን የግድቡ ባለቤት በማድረግ ተቃዋሚዎችን በተለይም አንድነትን የግብጽ መንግስት ተላላኪ አድርጎ መሳሉ ነውረኝነት ነው፡፡አንድነት አሁንም ኢትዮጵያ አባይን የመጠቀም ህጋዊና ታሪካዊ መብት ያላት መሆኑን አንድነት ያምናል፡፡አንድነት የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው የሚል አስተሳሰብ እንደሌለው በድጋሚ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

‹‹2007ን ለዲሞክራሲያዊ ለውጥ ›› በሚል መሪ ቃል ከመላ ሃገሪቱ ተወክለው የመጡ ከ450 በላይ የአንድነት አመራሮች/አባሎች በተገኙበት በዛሬው ቅዳሜ እለት ጠቅላላ ጉባዬውን ፓርቲው በደመቀ ሁኔታ እያካሄደ መሆኑን ከአዲስ አበባ ምንጮች ገልጸዋል:

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በቀጣዮ የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ መሳተፍ የምርጫውን ሜዳ መስፋትና መጥበብ ተከትሎ የሚወሰን መሆኑን አቶ ዘካሪያስ የማነብርሃን ገልጸዋል፡፡

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በቀጣዮ የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ መሳተፍ የምርጫውን ሜዳ መስፋትና መጥበብ ተከትሎ የሚወሰን መሆኑን አቶ ዘካሪያስ የማነብርሃን ገልጸዋል፡፡

ይህ በዛሬው እለት የተከፈተው የጠቅላላ ጉባዬ ስብሰባ ነገም የሚቀጥል ሲሆን እንዲሁም በተጨማሪ ዛሬ ቅዳሜ ለሊቱን የፐርቲው ስራ አስፈጻሚ ስለወደፊቱ የፓርቲው የትግል ስልትና ብቃት ያላቸው አባላትን በመመልመል የፓርቲውን አደረጃጀት አሁን ካለው በእጥፍ በማሳደግ በ2007ዓ.ም በሚደረገው ሀገር አቀፍ ምርጫ ህዝብን አስተባብሮ በአሸናፊ ለመውጣት በሚቻልባቸው ስልቶች ዙሪያ የጠለቀ ውይይት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል::

Andinet Party 4አንድነት ለጠቅላላ ጉባዬው የሚሆን አደራሽ ለማግኘት በየሆቴሉ እና አደራሽ አከራዮች ቢፈልግም ከገዢው ፓርቲ በተደረገ ማስፈራሪያና ተጽእኖ ማንም ሊያከራየው ፈቃደኛ ካለመሆኑም በላይ የህዝብ ንብረት የሆነውም የምርጫ ቦርድ አደራሹን ሰበብ በመፍጠር ከልክሎታል::

ከአፋር ክልል ተወክለው የመጡት የአንድነት አባል ሚከተለውን ብለዋል “ኢህአዴግ ወድቋል እሱን ለማስወገድ ያቃተን በኛ ችግር ነው፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል አንድነት ለአፋር ክልል የበለጠ ትኩረት ይስጥ” ብለዋል፡፡ ከኦሮሚያ ቦረና ዞን የተወክለው የመጡት አባል በበኩላቸው ኢህአዴግን ለመጣል እታች ድረስ የተዘረጋው መዋቅር መጠናከር እንዳለበት ተናግረዋል፡፡ ከቤንሻንጉል ክልል ተወክለው የመጡት አባል በ2005ዓ.ም ይደረጋል ተብሎ የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ በመቅረቱ ህብረተሰቡ ቅሬታ ማቅረቡን ተናግሯል፡፡

 

 

 

 

 

 

 

አንድነት ፓርቲና ዴሞክራሲያዊ ባህሉ
————————————
በነብዩ ኃይሉ
—————–
መጪዎቹ ሁለት የእረፍት ቀናት ለአንድነት ፓርቲ አባላት በናፍቆት የሚጠበቁ ሆነዋል ፤ ምክንያቱ ደግሞ ለወራት ዝግጅት ሲደረግበት የቆየው የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ቅዳሜና እሁድ (ታህሳስ 19 እና 20) የሚካሄድ መሆኑ ነው፡፡ የአንድነት ፓርቲ የቀደመ ተሞክሮ እንደሚያስረዳው ከፍተኛ የስልጣን አካል የሆነው ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያው ለወጉ የሚሰበሰብ አይደለም፡፡ ይልቁኑም በግልፅ የሚታይ የአመራር ለውጥ የሚደረግበትና ወሳኝ ፖለቲካዊ ውሳኔዎችም የሚስተናገዱበት ነው፡፡

አንድነት በ2001 እና በ2004 ባደረጋቸው ጠቅላላ ጉባኤዎች በግልፅ የሚታይ የአመራር ለውጥ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ይህ የፓርቲው አካሄድ በሀገር ደረጃም ቢደረግ የሚያስብሉ ዴሞክራሲያዊ ክዋኔዎችንም ያካተተነው፡፡ በሌሎች ፓርቲዎች ሲደረግ የማይስተዋል ቢሆንም አንድነት በሁለቱም ጉባኤዎች ሊቀመናብርቱን የመረጠው ጠንካራ ፉክክር ካደረጉ በኋላ ነው፡፡

በ2001ዓ.ም በተደረገው የፓርቲው የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ፣ ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው እና አቶ ተመስገን ዘውዴ ጠንካራ ፉክክር ካደረጉ በኋላ ጉባኤው ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳን በሊቀመንበርነት መርጧል፡፡

በ2004ዓ.ም በተደረገው የፓርቲው ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤም ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ ዶ/ር ንጋት አስፋው እና ኢ/ር ዘለቀ ረዲ ጠንካራ ፉክክር ካደረጉ በኋላ ጉባኤው የቀድሞውን የሀገሪቱን ፕሬዘዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳን የአንድነት ሊቀመንበር እንዲሆኑ መርጧል፡፡

አንድነት በመጪው ቅዳሜና እሁድ (ታህሳስ 19 እና 20) በሚያደርገው ልዩ ጠቅላላ ጉባኤም በግልፅ የሚታይ የአመራር ለውጥ ለማደረግ ተዘጋጅቷል፡፡ ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው፣ አቶ ተክሌ በቀለ እና አቶ ግርማ ሰይፉ የምረጡኝ ቅስቀሳቸውን ተያይዘውታል፤ አንድነትም ይህን ዴሞክራሲያዊ ባህሉ አንግቦ የኢትዮጵያን ህዝብ የስልጣኑ ባለቤት ለማድረግ የጀመረውን ጉዞ ይቀጥላል፡፡

እኔ ኣላውቅም ፈራሁ ጁሃር (ሄኖክ የሺጥላ)

$
0
0

የበደሌ ቢራ ፋብሪካ ከአዲስ አበባ 483 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ኢሉ-ኣባ-ቦራ ( Eloo The father of Holstein Friesian) ኢልባቡር ከተማ በሁለት መቶ ሃምሳ ሺ ስኩውር ሜትር ይዞታ ላይ ስራውን እንደ ኣውሮጳውያን ኣቆጣጠር በ 1993 ማከናወን የጀመረ ትልቅ የቢራ ማምረቻ ድርጅት ነው።

ኢሊባቡር መልካም ምድራዊ ኣቀማመጡም ሆነ ምድራዊ ልምላሜው፥ እንደ በቆሎ ፤ ገብስ፤ ጤፍ፤ የቅባት እሎች፤ ማር፤ ከነ ቦራ ደሞ ወተት፤ ቅቤ እና ወዘተ የሚዘራባት፤ የሚታጨድባት፤ የሚቆረጥባት፤ የሚታለብባት ሃገር እንድትሆን ኣድርጉዋታል።

Henok-Yeshitela-150x150

Poet Henok-Yeshitela

ኢሊባቡርን የጽሁፌ መንደርደሪያ አደረኩ እንጂ ዋናው ነጥቤ እሱ አይደለም። ዛሬ መናገር ወይም መጻፍ የፈለኩት ቴዲ አፍሮ በቅርቡ በመላው ኢትዮጵያ የሙዚቃ ዝግጅቱን እንዲያሳይ ወኪል የሆነውን የበደሌ ቢራን ያለመጠጣት አድማ ( boycotting) በመላው ኢትዮጵያ ይደረግ ዘንድ አንዳንድ ግለሰቦች የጀመሩትን ነገር ሰምቼ፤ ለምን በደሌን፤ ለምን ቴድን የሚል ጥያቄ ለሚጠይቁ፤ መልስ የሚመስለኝን ለመተየብ፤ ከተቻለም ለማሳየት መመኮር በመሻቴ ነው ።

ቴዲ አፍሮ በቅርቡ በ ጋዜጣ ላይ ስለ አድዋ ድል በሰጠው አስተያየት የተቆጡ፤ የተቀየሙ ግለሰቦች፤ ቴዲ አፍሮ ጥቁር ሰው ብሎ ንጉስ ሚኒሊክን፤ ከዛም በላይ አድዋ ድልን በመዘከሩ የተበሳጩ የህብረተሰብ አካሎች፤ ቴዲ አፍሮ ከዚህ ቀደም ጃ ያስተሰርያል ብሎ በመዝፈኑ ቂም የቁዋጠሩ ሰዎች፤ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በሊግ ኦፍ ኔሽን በ 1936 የኢጣልያንን የተለከለ የኬሚካል መሳሪያ መጠቀምን በመቃወማቸው፤ ኢትዮጵያን የ ዩናትድ ኔሽን ኣባል በማድረጋቸው፤ ቅራኔዎችን አብርደው ያፍሪካን ህብረት በመመስረታቸው፤ ለነዚህ ጉልህ አስተዋጾዎቻቸው በመዝፈኑ፤ ለነዚህ ለተጠቀሱት መልካም ስራቸው መታሰቢያ የጭንቅላቱ ውጤት የሆነውን ሙዚቃ በማበርከቱ፤ ቴዲ አፍሮ ፤ አቀንቃኝ ና አዝማሪ ፤ ገጣሚና ስዓሊ፤ ሃያሲና ደራሲ፤ ጸሃፊ ተውኔቱና ብላታው፤ አፉን በለጎመበት ዘመን፤ በብእሩ የታሪክ ጋሻ፤ በግጥሙ ለቆሰለ ታሪክ ማገገሚያ፤ በዘፈኖቹ ( ከ ማሊ ሱፊዎች ባልተናነሰ መልኩ) የነብስን ክር እየተጫነ ያላስለቀሰው፤ ያላስተከዘው፤ ሰው እንደሌለ የገባቸው ሰዎች፤ በይበልጥም የአድዋ ድል፤ የጥቁር አንበሳዎች ድል መሆኑን ያሳየበት በመሆኑ እና ይህም የሚያማቸው ሰዎች፤ ዛሬ በደሌ ቢራ ቴዲ አፍሮን ስፖንሰር ስላደረገ፤ በደሌ ቢራን ያለመጠጣት አድማ ጠርተዋል። አሁን ቴዲ አፍሮን አብዶ በረንዳ ( የጫት ማከፋፈያ በረንዳ ነው) ቢሆን ስፖንሰር ያረገው ምን ሊሉ ነበር።። ባረገው እና የተከታዮቻቸውን መልስ ባየን። አንድ ጊዜ ቆይ ጠብቁኝ ሳቄ መጣብኝ ያለው ተናጋሪ ማን ነበር።

አዲሱ የቴዲ አፍሮ አልበም ( ጥቁር ሰው) የብዙዎቹን ኢትዮጵያዊያኖች ድምጽ ያስገኘለትን ያህል፤ ንጉስ ሚኒሊክ በድሎናል፤ ጡታችንን ቆርጦዋል፤ ወዘተ ወዘተርፈ ለሚሉት ደሞ፤ ከሚኒሊክ መፈጠር፤ ከታሪክ አንቅጽነቱና አኩሪ ገድሉ ጋር የጀመሩትን እጹብ ጸብ ውሃ የሚደፋበት በመሆኑ፤ ጠላት ሊያፈራበት እንደሚችል መገመት ብዙም አይዳግትም። እናም እነዚህ ሰዎች ቀደም ብዬ እንደ ጠቀስኩት፤ በደሌ ቢራን ያለመጠጣት አድማ እናድርግ እያሉ ነው። ልክ ናቸው፤ ህዝብ በጥላቻም በቢራም ሰክሮ እንዴት ይሆናል፤ ባንዱ ብቻ ይበቃልና።

በነገራችን ላይ ይህንን አድማ ለማስመታት ከሚራወጡት እና ከሚሯሯጡት ሰዎች መሃከል አንዱ ጁሃር መሀመድ መሆኑን ሰምቼ አፍሬ ጥፍሬ ውስጥ ልገባ ነበር። ባንድ ወቅት ይሄ ወጣት ፖለቲከኛ ስለ ራሱ ሲናገር “እኔ እናቴ መንዜና የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ነች አባቴ ደሞ ኦሮሞና ሙስሊም ነው ፤ ታዲያ ከኔ በላይ ኢትፖጵያዊነትን የሚወክል ምንነት ኣለ ወይ” ብሎ ነበር። መልሱ ሊሆን ይሚችለው ጁሃርዬ በውነትም የለም፤ እንዳንተው አቶ መለስም እኮ የተላቀቀ ነገርን ማጣበቅ የሚችል (ኡሁ የሆነ) (UHU…glue) ደም ነበራቸው፤ ግን ደሙ ሳይሆን የደሙ ባህሪ ነው ወሳኙ ነገር። የተሸከምነው ደም ሳይሆን በውስጣችን ያፋፋነው ስብዕና ነው ማንነት ፤ ማንነት ስራ ነው እንጂ አንተ እንዳልከው የ-ኢ-ተጎራባች ዘር ደም ውህደት (ኬሚስትሪ ውጤት አይደለም)፤ ክርስቶስ ( ኤሳው… ኣለይሁ ሰላም) በ-በረት ተወለደ ብለን እናምናለን፤ ግን እንደ ሰብኣዊ ፍጡር በ-በረት መወለዱ ሳይሆን ሰው ሆኖ ሲኖር ያደረገውን ነገር ነው የምናስበው፤ ስለ ነብዩ ሙሃመድ (ሰ.አ.ወ) ኣንድ ሙስሊም ሲያስብ ስለ ዘራቸው ሳይሆን ስለ ስራቸው ነው የሚያስበው ብዬ አስባለሁ ።

ባንድ ወቅት ይሄው ሰው፤ ፹ ከ ፻ የሚሆነው የሃገሬ እስላም ኦሮሞ ነው፤ እናም የኦሮሞ ህዝብን ኢምፓወር ማድረግ፤ እስልምናን ኢምፓወር እንደማረግ ነው አለን፤ ለመስማት አይደል የተፈጠርነው እናም ሰማነው፤ ባሜጃ አለን ዝም ብለን ሰማነው፤ ቀጥሎም ኢትዮጵያ አውቶ ኦፍ ኦሮሚያ አለን እሱንም ሰማነው። በነገራችን ላይ ኢትዮጵያ ኣውት ኣፍ ኦሮሚያን ወደ ፈርንጅኛ ስቀዳው ( the child give birth of her mother) ኣይመስላችሁም ? ለመተርጎም የተገደድኩት የመጀመሪያው ራሱ እንግሊዘኛ መሆኑን ስለተጠራጠርኩ ነው። ለነገሩ ስታንፈርድና ኮሎምቢያ ዩንቨርስቲ እኮ መፈክር አያስተምሩም።

እና ዛሬ በደሌ መጣ እና ወንድሜ ጁሃር ሰማኒያ ከመቶ ካለው ሃሳብ ጋ ግንባር ለግንባር ተጋጨ ( head on collusion) እናም ሁለት የሚጋጩ ነገሮችን እንግዲህ እናስተውላልን።

፩) መቼም ፹ ከመቶው እስላም ኦሮሞ ነው ብለኽን፤ አንተም በዘር ብቻ ሳይሆን በእምነትም ጭምር ጠበኽ፤ ኣልገባኝም ታዲያ እንዴት ነው፤ እነማን ቦይ ኮት እንዲያረጉልኽ ነው ጥሪውን ያቀረብከው፤ ፳ ፐርሰንቱ እስላም ያልሆነው ኦሮሞ ? ደሞ ከ ፹ ከመቶ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ውስጥም ቢሆን አዲስ የበደሌ አድመኛ ማግኘት ይቸግራል ብዬ አስባለሁ፤ ምክኒያቱም እነሱ ላንተ ሲሉ ሳይሆኑ ለዲናቸው ሲሉ ድሮም እንዲህ አይነቱን ነገር ይነኩት ነበር ብዬ አላስብም፤ በፍጽም አያደርጉትም፤ ታዲያ የማይጠጡ ሰዎችን ነው አድማ የጠራነው፤ ወይስ ሙሉ የኢትዮጵያዊነት ማሳያ ምሳሌ እንድትሆን ያደረገችህ የመንዜዋ እናትህን ዘመዶች፤ እኔ ኣላውቅም ፈራሁ ሄኖክ ነው ያለኝ የልጅነት ጉዋደኛዬ፤ ባንድ ትልቅ የውሃ ጉድጉዋድ ውስጥ እንሹለክ ስለው። እኔ አላውቅም ፈራሁ ጁሃር።

ዛሬ ጀርመን ያላትን ቅርጽ እንድትጠብቅ ወይም እንዲኖራት ያደረገው ኦቶ ቮን ቢስ ማርክ፤ የደም ትግል ውጤት ነው። ታዲያ ጀርመኖች በ ቢስ ማርክ ተናደው ፒሊሲነርን ( የጀርመን ታዋቂ ቢራ ነው) ቦይ ኮት እናርግ አላሉሉም። በፈረንሳይ እንዲህ የሚባል ታሪክ አለ፤ በአሜሪካም፤ ኣረ ሆመር በጥንታዊያኖቹ የግሪክ ዘመን ስለነበረው ጦርነትም ጽፎዋል፤ ስለ ስርኣቱ፤ ስለ አገማምኖን እና የወንድሙ መንግስት፤ ስለ ሄለናዊው ስርዓት፤ ከዚያም በሁዋላ እነ ዳንቴ ስለ ጻፉት ስለ ዲቫይን ኮሜዲ፤ ፍሬድሪክ ዊልሃልም ኒቺ ስለተራቀቀበት የማህበረሰብ ስነ ልቦና፤ እነ አልበርት ካሙ ስለጻፉለት የፈረንሳይ ማህበረስብ እና በየስራቶቹ ውስጥ ስለ ነበርው ፍዳ፤ እነ ልዮ ቶሎስቶይ በሰላ ብእራቸው ስለዘገቡት የሩሲያ የጭቆና ቦለቲካ፤ እነ ፓብሎ ፒካሶ ጉሬንሽያ ብለው ስለገለጹት የስፔን ከተማ ስለ ስንቱ ለዚህ ለወጣቱ ፖለቲከኛ እንንገረው እስኪ ባክህ ጁሃርዬ ገረፍ ገረፍ አርጋቸው (በቃ እንደውም ለዚህ ክረምት ለፐርሰናል ዲቨሎፕመንት…ትመለከታቸው ዘንድ እጠይቅሃለሁ (ማሳሰቢያ በኣብዛኛው በአማራ ጻሀፊ አይደልም የተጻፉት ቢሆኑም ደሞ ኣነተ ሃምሳ ፐርሰንት አማራ አይደለህ እንዴ፤ የምሬን እኮ ነው)

በታሪክ ላይ ጥላሸት መቀባት በፍጹም ለማንም አይሳካም፤ ወደድንም ጠላንም፤ ጠቅልለን የምንጎርሰውን እንጀራ የፈጠሩት አባቶቻችን ናቸው፤ ለሆዳችን ያለን ቅርበት ለታሪካችንም ይኑረን። ቴዲ እንዳለው ክፉውን በክፉ ለመመለስ ማሰብ ሌላ ክፉነት ነው። ሁለቱ ደሞች እንደ ደም ይሰሩ፤ ያስቡ ዘንድ ሰው እንሁን።

ሄኖክ የሺጥላ

 

 

ፍትህ የተጠማች ነብስ (Video)

ሆቴል ውስጥ የተደባደቡት የብሔራዊ ቡድናችን ተጫዋቾች ሲሳይ ባንጫንና አበባው ቡታቆ ተቀጡ

$
0
0

Abebaw-Butakoየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን ጥፋት ፈፅመዋል ባላቸው ተጫዋቾች ሲሳይ ባንጫ እና አበባው ቡታቆ ላይ የገንዘብ ቅጣት መንግስታዊው ሚዲያ ራድዮ ፋና ዘገበ። ሲሳይ ባንጫ የአስር ሺህ አበባው ቡታቆ ደግሞ የአምስት ሺህ ብር ቅጣት ነው በፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የተወሰነባቸው።
እንደ ፋና ዘገባ ተጫዋቾቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ካላባር ላይ ከናይጄሪያ አቻው ጋር ከተጫወተ በኋላ ቡድኑ ባረፈበት ሆቴል ውስጥ በመጣላታቸው ነው ቅጣቱ የተወሰነባቸው። ፌዴሬሽኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው ግብ ጠባቂ ሲሳይ ባንጫ ከቡድን አጋሩ ጋር መጣላቱን በማመን ይቅርታ ጠይቋል።
ራድዮው ጨምሮም በተመሳሳይም ተከላካዩ አበባው ቡታቆ የፀቡ መነሻ እንዳልሆነ በመግለፅ ነገር ግን ከቡድን አጋሩ ጋር መጣላቱ ስህተት መሆኑን አምኖ ይቅርታ ጠይቋል።
የፌዴሬሽኑ አመራሮችም በወቅቱ በተጨዋቾቹ የተፈፀመውን የስነ ምግባር ግድፈት በተመለከተ የምስክርነት ቃላቸውን መስጠታቸውንም ነው መግለጫው ያመለከተው። ከዚህም በመነሳት በፌዴሬሽኑ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት የገንዘብ ቅጣቱ የተወሰነባቸው ሲሆን ወደፊትም እንዲህ ዓይነት
ከባድ ጥፋት እንዳይፈፅሙ ከባድ ማስጠንቀቂያም እንዲደርሳቸው መወሰኑን ነው ፌዴሬሽኑ መግለጹን ራድዮው ዘግቧል።

አዲስ አበባ በቤት ኪራይ ንረት እየተናጠች ነው

$
0
0

ዜና ትንታኔ ከብርሃኑ ፈቃደ
(ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደጻፈው)

የመኪና ራዲያተር ጥገና ባለሙያ ነው፡፡ በኪራይ ምክንያት በሚሠራበት ሰባተኛ አካባቢ የተደረገበት ጭማሪ አስደንጋጭ ሆኖበት ሲበሳጭ ከርሟል፡፡ አንድ ሺሕ ብር ይከፍልበት የነበረው ቤት፣ ‹‹ብዙ ግብር መጥቶብኛል፤ ስለዚህ ሁለት ሺሕ ብር ተጨማሪ ክፍያ መደረጉንና የኪራዩ ዋጋ ሦስት ሺሕ ብር መሆኑን እንድታውቀው፤›› የሚል ቀጭን መልዕክት ደርሶት ከአከራዩ ጋር ተጨቃጭቆ መክረሙን የሚናገረው ወጣቱ ሰው፣ አልታይ ዘለቀ (ስሙ ተቀይሯል) ነው፡፡

ለጭማሪው በአከራዩ የቀረበውን ምክንያት የማይቀበለው አልታይ፣ ‹‹እንዴትም ተብሎ ግብር ቢጨምር፣ ከመንገድ ዳር ርቆ የትኛውም ደንበኛ ቤቱን አይቶ ለመምጣት በማያስችለው አካበቢ ላይ ለሚገኝ ቤት፣ ሥራው በተባራሪ እየተሠራ፣ ሥራውን ለሚያመጡ ደላሎች ኮሚሽን እየከፈልኩ ለምሠራው ሥራ በአንድ ጊዜ ይሄን ያህል ጭማሪ ማድረግ ወዴት እየወሰደን እንደሆነ ግራ ገብቶኛል፤›› ሲል ይኮንናል፡፡ የአንድ ልጅ አባት የሆነው አልታይ፣ የራሱንና የባለቤቱን ቤተሰቦች ጨምሮ ሦስት ቤተሰብ የሚያስተዳድርበት ይህ ሙያው ከዚህ ሁሉ ቤተሰብ ቀለብና ወጪ ተርፎ በአንድ ጊዜ ጭማሪ በተደረገበት ልክ የሚበቃ ገቢ ካላገኘበት፣ ወደ ክፍለ አገር አለያም ወደ ዓረብ አገር ለመሰደድ ማሰቡን ተናግሯል፡፡
appartment in addis
የአልታይ ጓደኛ የሆነው ሌላው አስተያየት ሰጪ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ትምህርት ቤት ከፍቶ መሥራት ከጀመረ ሦስት ዓመታት መቆጠራቸውን ይገልጻል፡፡ ያለቻቸውን ገንዘብ አሟጥጠው፣ ከጥቃቅንና አነስተኛ ገንዘብ ተቋማት ተበድረው የሚያንቀሳቅሱትን ትምህርት ቤት የከፈቱት ሕንፃ ከግለሰብ ተከራይተው ነው፡፡ ለኪራይ በዓመት ከአምስት መቶ ሺሕ ብር በላይ ይከፍላሉ፡፡ ማስፋፊያ ለማድረግ ሌላ ተጨማሪ የግለሰብ ሕንፃ መከራየት ግድ ሆኖባቸው መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ ከአንደኛ ክፍል እስከ 12ኛ ለማስተማር የሚያስችሉ ክፍሎችን ለማሟላት የግለሰብ ሕንፃ በውድ ዋጋ መከራየትና መሥራት አማራጭ የለውም ይላሉ፡፡ ሥራው እንዲህ ያለው አላስፈላጊ ጫና ባይኖርበት ኖሮ የበለጠ ጥሩ ሥራ ለመሥራት ያመቻቸው እንደነበርና ይበልጥ የሰው ኃይል ቀጥረው፣ በርካታ ተማሪዎችን ማፍራት የሚያስችላቸውን መንገድ የቤት ኪራይ ዋጋ እንዳራቀባቸው ተናግረዋል፡፡

መንግሥት ለትምህርት ዘርፍ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ ቢያስታውቅም፣ በደህናው ጊዜ ቦታ በርካሽ አግኝተው ሕንፃ የሠሩ ሰዎች በኪራይ ከሚያግበሰብሱት ገቢ የማያገኘውን ታክስ፣ እኒህ ተከራዮች ከሚሰጡት የትምህርት አገልግሎት ከፍተኛ ታክስ ይሰበስባል፡፡ ሆኖም ትህምርት ቤት መሥሪያ ቦታ ማግኘት የማይታሰብ እንደሆነባቸው የሚገልጹት አስተያየት ሰጪ፣ የሊዝ ግዥ ለማድረግ የሚቀርበው መነሻ ዋጋ በአስገራሚ ሁኔታ በካሬ ሜትር እስከ አሥር ሺሕና በዚያም በላይ በመድረሱ መቸገራቸውን ይገልጻሉ፡፡ መንግሥት ለትምህርት ዘርፉ እንደቆዳና ሌሎች ፋብሪካዎች የሰጠውን ማበረታቻ ሲሰጥ ማየትም አልቻንም ይላሉ፡፡ በሊዝ ጨረታ መነሻ ዋጋ መሬት እንደልብ ከተማው ላይ ለእነዚህ ዘርፎች ሲሰጥ ይታያል፡፡

ከቻይናና ከሌላውም አገር ለመጡ ‹‹የውጭ ባለሀብቶች›› የሚሰጠው ድጋፍ በትምህርቱ ዘርፍ አገልግሎት ሰጥተው፣ ብዙ ሠራተኛ ቀጥረው ለሚያሠሩትና ከፍተኛ ግብር በመክፈል አስተዋጽኦ ለሚያበረክቱት ሰዎች ምንም ዓይነት ድጋፍ ከመንግሥት እያገኙ እንዳልሆነ በመግለጽ መቸገራቸውን አስታውቀዋል፡፡ ሕንፃ አከራይ እንዲያገኝ የተመቻቸለትን ጥቅም፣ ለብዙ ሰው የሥራ ዕድል አስገኝተውና አገልግሎት ለሕዝቡ ሰጥተው የሚሠሩ ሰዎች እንደአስቷጽኦዋቸው የሚጠቀሙበትን ዕድል አለማግኘታቸውን ይገልጻሉ፡፡ መንግሥት ለአከራይ እንጂ ለሠርቶ አሠሪና በኢኮኖሚው ውስጥ እሴት ጨማሪ ለሆኑ አካላት በመሬት አቅርቦት የሚያድርገው ድጋፍ ከወለል በታች መሆኑን በመግለጽ ይተቻሉ፡፡

‹‹የመንግሥት የመደብ ጨቋኝነት ሚና››

በአዲስ አበባ ሕንፃ የገነቡ አብዛኞቹ ከመንግሥት የ70 ከመቶ ብድር አግኝተው፣ መሬት ተመርተው ወይም በርካሽ ተጫርተው በሊዝም ሆነ በይዞታ ከገዙ በኋላ ያለምንም ድካምና ውጣውረድ በመንግሥት ገንዘብ በገነቡት ሕንፃ ያለሐሳብ ሀብታሞች እንዲሆኑ በመንግሥት ዕድሉ የተሰጣቸው ናቸው፡፡ መኪና ገጣጥመው፣ ትምህርት ቤት መሥርተው፣ በፋብሪካ አምርተው ለመሥራት የሚጣጣሩ ሰዎች የማያገኙትን የገቢ ዝቆሽ፣ ሕንፃ አከራዮች በመንግሥት ተባባሪነት የሚያገኙትን ጥቅምና የዳጎሰ ገቢ በመመልከት፣ አንድ ሕንፃ በባንክ ብድር በመሥራትና ሕንፃውን ለብድር ማስያዣነት በመዋል ገርበብ ባለው የብልጽግና በር በኩል ሾልከው የተመነደጉ ጥቂት አይደሉም፡፡

በአገሪቱም ሆነ በአዲስ አበባ መዲናም መንግሥት የሚፈልገውን ያህል የማኑፋክቸሪንግ ወይም የኢንዱስትሪ መስኮች አለመስፋፋት ችግሮች መንስዔ ከሆኑ ምክንያቶች መካከል እነዚህ አቋራጭና በቀላሉ የዕድሜ ልክ ባለሀብት መሆን የሚቻልባቸው መንገዶች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ አንድ ባለፋብሪካ ወይም ባለትምህርት ቤቱ ባለጉዳይ እንደሚጠቅሱት ሥራቸው በበርካታ ሰዎች ትከሻ ላይ የወደቀ ነው፡፡ ብዙ ሠራተኛ ተቀጥሮና እሴት ተጨምሮ የሚሠራው ሥራ ትርፍ ማስገኘት የሚጀምረው ከፕሮጀክቱ ትግበራ አራት ወይም አምስት ዓመታት በኋላ ሊሆን ይችላል፡፡ በአንፃሩ ሕንፃ ሠርተውና ሸንሽነው የሚያከራዩ ግን ቦታ አጥቶ የተቸገረ ነጋዴ ወይም ሌላው አካል በካሬ ከ500 እስከ 5,000 ብርና ከዚያም በላይ እየከፈለ ለመሥራት የሚገደድ ጭሰኛ ሆኗል ይላሉ፡፡ አከራዮች ከኪራይ በሚሰበስቡት ገንዘብ የባንክ ዕዳ ከፍለው ሀብታቸው የማይነጥፍ ቱባ ሀብታሞች ይሆናሉ፡፡

ስለዚህ ፋብሪካ ከመገንባትና ለኢኮኖሚው እሴት የሚጨምሩ ዘርፎች ላይ ከመሠማራት ይልቅ በአቋራጭና በአጭር መንገድ ሀብታም የሚያደርጉ አማራጮች በመንግሥት በኩል ስለተመቻቹ፣ ለምን ብለው ይደክማሉ፤ ለነገሩ የደከሙትስ ምን አተረፉና የሚል መከራከሪያ በከተማው በሰፊው የሚደመጥ ሙግት ሆኗል፡፡

መምህር በቀለ የተባሉ በጡረታ ላይ የሚገኙ መምህር በአንድ ወቅት በኅብረተሰብ ሳይንስ ትምህርት ወቅት ስለመንግሥት ሥርዓትና አወቃቀር ሲያስትምሩ ‹‹መንግሥት የመደብ መጨቆኛ መሳሪያ ነው፤›› በማለት ይገልጹ ነበር፡፡ ይህም ሲባል የበላይ መደብ ያላቸው፣ በካፒታልና በገንዘብ አቅማቸው የተነሳ የመንግሥትን አገልግሎት በቀላሉ ለማግኘት የሚቻላቸው መሆናቸውን ለማመልከት የሚጠቀሙበት አገላለጽም ነው፡፡

ቤት መግዛት ባትችል ትከራያለህ፣ መከራየት ባትችል ግን?

በአሜሪካ የኪራይ ቤቶችን በማስመልከት ከጥቂት ሳምንታት በፊት አንድ ጥናት ይፋ ተደርጎ ነበር፡፡ በኪራይ ቤቶች ዙሪያ በሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲና በአጋሮቹ የተደረገው የጋራ ጥናት እንደሚያመለክተው፣ የቤት ኪራይ ዋጋ እ.ኤ.አ. ከ1980ዎቹ ጀምሮ እየጨመረ ይገኛል፡፡ በአንፃሩ የዜጎች ገቢ በየጊዜው እየቀነሰና እያነሰ መምጣቱን ተመልክቷል፡፡ የሀርቫርድ የኪራይ ቤቶች ጥናት እንደሚያረጋግጠው፣ ከሆነ ከ11.3 ሚሊዮን ያላነሱ አሜሪካውያን የራሳቸው ቤት ሊኖራቸው የሚችልበት አቅም የላቸውም፡፡ የኪራይ ቤት ጥገኛ ናቸው፡፡ በዚህ ሳቢያ ከግማሽ በላይ ገቢያቸውን ለኪራይ በመክፈል ለአስከፊ ወጪ የተዳረጉና ልፋታቸውን ለኪራይ የሚገብሩ መሆናቸውን ጥናቱ አረጋግጧል፡፡ ከእነዚህ ትንሽ ዝቅ ያለ ገቢ ያላቸው ግለሰቦች ዝቅተኛ የሚባለው የኪራይ ወጪያቸው፣ የገቢያቸውን 30 ከመቶ ለኪራይ የሚከፍሉ ናቸው፡፡

ከሁለት አሜሪካውያን አንዱ በቤት ኪራይ ወጪ ናላው የሚናውዝ መሆኑን የሚጠቁመው ጥናት፣ በአሁኑ ወቅት ለከፍተኛ የኪራይ ጫና ከተዳረጉት 12 ሚሊዮን አሜሪካውያን ባሻገር 21.1 ሚሊዮን አሜሪካውያን ለቤት ኪራይ ወጪ መሸፈኛነት ገቢያቸውን በማሟጠጥ ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡

ጥናቱ ሰፊና አስገራሚ ዕውነታዎችን ማስነበቡን ይቀጥላል፡፡ አሜሪካውያን በፌደራል መንግሥታቸው ደረጃ በሰዓት በአማካይ የሚያገኙት ገቢ 7.5 ዶላር (በወቅቱ ምንዛሪ ቢመታ 150 ብር መሆኑ) ነው፡፡ ሆኖም ባለሁለት መኝታ ክፍል ደህና መኖሪያ ቤት መከራየት የሚፈልግ አሜሪካዊ፣ በየትኛውም የአሜሪካ ግዛቶች ይህን መሰል ቤት መከራየት የሚችለው በሰዓት ቢያንስ 20 ዶላር (በሰዓት 400 ብር ያህል) ገቢ ማግኘት የቻለ እንደሆነ ነው ሲል ጥናቱ ማረጋገጫውን አስፍሯል፡፡ ከሁለት መኝታ ቤት ያነሰ ግን ደግሞ ደህና ሊባል የሚችል ቤት መከራየት የሚፈልግ ሰው የሰዓት ገቢው 12 ዶላር መሆን ይጠበቅበታል፡፡ ስለዚህ በየትኛውም የአሜሪካ ግዛት በሰዓት 7.5 ዶላር ዝቅተኛውን ገቢ የሚያገኝ አንድ ዜጋ ደህና የሚባለውን ቤት ተከራይቶ መኖር አይችልም፡፡

ኪራይ የሚያንረው ባለንብረቱ ነው

የኢትዮጵያ በተለይ የአዲስ አበባ ሁኔታ ይህንን ይመስላል፡፡ ኮንዶሚኒየም ተከራይቶ ለመኖር የሚችለው ሰው ወርኃዊ ገቢው ቢያንስ ከአምስት ሺሕ ብርና ከዚያም በላይ መሆን እንዳለበት ጥናት ማድረግ ሳያስፈልገው የሚታወቅ ነው፡፡ በከተማው ትልቁን የገቢ ምንጭ የሚበዘብዘው የኪራይ ዋጋ እንደሆነ ተራ አባወራ ብቻም ሳይሆን ሕንፃ ተከራይተው ቅርንጫፎቻቸውን የሚስፋፉ ባንኮች ሳይቀር የሚገነዘቡት ነው፡፡ የባንክ አገልግሎት እምብዛም በማይፈለግባቸው የአዲስ አበባ ጠረፍ አካካቢ የተከፈቱ የባንክ ቅርንጫፎች ሲናገሩት የሚደመጥ ነው፡፡

በአንፃሩ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ቢሮ ለመከራየት ሁለት ጉዳዮች ቦታ እንዳላቸው የሚገልጹት የኢኮኖሚ ባለሙያው ዶክተር ደምስ ጫንያለው ናቸው፡፡ አንደኛው ቤቱ የሚገኝበት ቦታ ለኪራይ ዋጋው ከፍተኛ መሆን አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ ‹‹ዓይን ቦታ›› ተብሎ በልማድ የሚጠቀሰው አገላለጽ በተለይ በንግድ ሥራ ለተሰማሩ ሰዎች የተለመደ ሲሆን፣ ገበያ እስካለውና ወጪያቸውን ሸፍኖ ትርፍ እስካስገኘ ድረስ፣ ለትራንስፖርትና ለመሳሰሉት አገልግሎቶች ያለው ምቹነት እየታየ ዋጋው እንደሚለያይ ከምሁሩ ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡

ሌላኛው ዋጋውን ውድና ተገቢ ሊያደርገው የሚችለው ምክንያት የቤቱ ወይም የንብረቱ ባለቤትነት ነው፡፡ በግለሰቦች ይዞታና በተቋማት መካከል ባለው ልዩነት መካከል የዋጋው ከፍተኛነትና ዝቅተኛነት ሊንፀባረቅ እንደሚችልም ዶክተር ደምስ ይገልጻሉ፡፡

በኢኮኖሚ ሙያቸው የማማከርና የጥናት ሥራዎችን የሚያካሂዱት ዶክተር ደምስ፣ የኪራይ ዋጋ ከውል ውጭ ያለአግባብ ተጨምሮባቸው የተከራዩትን የግለሰብ ቤት ለመልቀቅ መገደዳቸውን ገልጸዋል፡፡ ‹‹ከግለሰብ ተከራይተን ነበር የምንሠራው፡፡ ስድስት ወር እንኳ ሳንቆይ በአንድ ጊዜ 35 ከመቶ ያህል ጨምረውብናል፤›› ያሉት ዶክተር ደምስ፣ አብዛኞቹ ግለሰቦች ሀብቱ ስላላቸው ዋጋ እንዳሻቸው ይጨምራሉ እንጂ ገበያው ላይ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ አይተውና ጥናት አድረገው የሚጨምሩ እንዳይማስላቸውም ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ለአንድ ዓመት በውል ተዋውለውና ቅድሚያ መክፈል የሚጠበቅባቸውን ከፍለው ሥራ ቢጀምሩም፣ ከውል ውጭ በተደረገው ጭማሪ ቅር ተሰኝተው ሌላ አካባቢ ፈልገው ለመግባት ተገድደዋል፡፡

የአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ለአብዛኛው ሰው የሚቀመስ አለመሆኑን ምሁሩ ብቻም ሳይሆን ነዋሪዎችና ነጋዴዎች የሚስማሙበት ሀቅ ነው፡፡ ለዚህም ይመስላል አንዳንድ ሰዎች ‹‹ከፒያሳና ከቦሌ ዕቃ መግዛት ለነጋዴው የቤት ኪራይ እንደመክፈል ይቆጠራል፤›› ሲሉ የሚደመጡት፡፡ በእነዚህ አካባቢዎች የሚሸጡት ዕቃዎች መርካቶና ሌላው አካባቢ ከሚሸጡት የተለዩ ሆነው ሳይሆን በዋጋቸው የማይቀመሱ ሆነው ስለሚገኙ የሚነገር አገላለጽ ነው፡፡ በከተማው ለሱቅ ኪራይ በካሬ የሚከፈለው ክፍያ በአስገራሚ ፍጥነት እየጨመረ መጥቷል፡፡ በቦሌ አካባቢ ከሚገኙ ሕንፃዎች መከራየት የሚፈልግ ነጋዴ፣ በአማካይ በካሬ ከሁለት ሺሕ እስከ ሦስት ሺሕ ብር ይጠየቃል፡፡ አምስት መቶ ብርና ከዚያ ያነሰ ዋጋ በካሬ የሚከፈልባቸው ሕንፃዎች ቢኖሩም፣ አዳዲስ የተሠሩት ግን በዚህ ዋጋ የሚደፈሩ አይደሉም፡፡ አካባቢ የቤት ኪራይ ዋጋን በዚህ መልኩ ሊወስን ቢችልም፣ የግል አከራዮች የሚያደርጉት ጭማሪ ባለንብረትነታቸው ላይ ያጋድላል፡፡

በአንፃሩ አከራዮች የየራሳቸውን አካሄድ እንደሚከተሉና በርካታ ወጪዎችን በማውጣት፣ ጥሪታቸውን አሟጠው ለገነቡት ሕንፃ ተመጣጣኝና ተከራዮችንም የማይጎዳ የኪራይ ዋጋ እንደሚጠይቁ ይሟገታሉ፡፡ በተለይ ከመገናኛ እስከ ሃያ ሁለት ባለው መስመር ሕንፃዎቻቸውን የሚያከራዩ ባለንብረቶች፣ በመንገድና በባቡር መስመር ግንባታ ምክንያት ሥራ በመጥፋቱ ምክንያት ኪራይ በግማሽ የቀነሱ መሆናቸውን ይገልጻሉ፡፡ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣንም በመንገድ ሥራው ምክንያት ሥራ ቀንሶባቸዋል ባላቸው ድርጅቶችና አነስተኛ ነጋዴዎች ላይ የሚጥለው ታክስ ላይ አስተያየት ሲያደርግ ተስተውሏል፡፡

በአዲስ አበባ ኬሻ በጠረባ ከሚተኛባቸው የጎጃም በረንዳ፣ የአሜሪካ ግቢ፣ የሰባተኛ ሰፈሮች አንስቶ እስከ ቦሌ፣ ገርጂ፣ ቤቴል የመሳሰሉት አካባቢዎች ቤት የሚከራይባቸው ናቸው፡፡ ኬሻ በጠረባዎቹ ቤት ለአዳር ያከራያሉ፡፡ ኬሻ በጠረባ እየተባሉ የሚታወቁት ቤቶች፣ ድሮ ድሮ ኬሻ፣ አሁን አሁን ካርቶን ተነጥፎ ለአንድ አዳር ሰው እንደጣውላ ተደርድሮ የሚታደርባቸው ቤቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ቤቶች ድሮ ከነበራቸው ማደሪያ የለሽ ደንበኛ ባሻገር፣ ከየክፍለ አገሩ ይጎርፉ የነበሩ የዓረብ አገር መንገደኞች የሚያገኙት ገቢ አስተማማኝ ሆኖላቸው ቆይቷል፡፡ ዓረብ አገር የሚሄዱ ሴቶች እንደከተማው ማደሪያ ቢስ ሰካራም ሳይሆን እጥፍ ከፍለው ያድሩ እንደነበር ሪፖርተር ያነጋገራት የጎጃም በረንዳ ኬሻ በጠረባ አከራይ ሺመታ አሕመድ ታስታውሳለች፡፡ አሁን ግን በጎጃም በረንዳ ኬሻ በጠረባ እያበቃለት መምጣቱን የሚጠቁም አካሄድ በባቡሩ መስመር ግንባታ እየታየ ነው ትላለች፡፡ ከፊት ለፊት የነበሩት ሱቆች አብዛኞቹ በመፍረሳቸው፣ አልጋ ያከራዩ ከነበሩት ቤቶች አንዳንዶቹ ለሱቆች ዕቃ ማከማቻነት እየዋሉ መምጣታቸውን ትገልጻለች፡፡ አብዛኞቹ ግን ለአዳር ከሚያከራዩዋቸው ቤቶች ውስጥ አብረው የሚኖሩ በመሆናቸው፣ ቤቶቹ ሲፈርሱባቸው ዕድል ከቀናቸው ኮንዶሚኒየም ቤት የሚቀየርላቸው በመሆኑ የገቢ ምንጫቸው ላይ አደጋ እንደተጋረጠበት ሥጋት የገባቸው ናቸው፡፡

ከእነዚህ ባሻገር ያሉት የገርጂና የቦሌ ቤቶች ቅንጡ ናቸው፡፡ የሚከራዩት በድረ ገጽ በሚለቀቁ ማስታወቂያዎች ሲሆን፣ ከ800 (16,000 ብር) እስከ 4,000 ዶላር (80,000 ብር) ድረስ የኪራይ ዋጋ የሚጠየቅባቸው ቤቶችም በአዲስ አበባ ጥቂት አይደሉም፡፡ አብዛኞቹ ቦሌ፣ ኦሎምፒያ፣ ገርጂ (በይበልጥ ሰንሻይን አፓርታማዎች)፣ ካዛንቺስ አካባቢ የሚገኙ ቤቶች ባለአንድ፣ ባለሁለትና ባለሦስት መኝታ መሆናቸው እየተገለጸና ዘመናዊ የቤት ውስጥ ቁሳቁስ እንደተሟላላቸው የሚገልጹ ማስታወቂዎች የሚያጅቧቸው ናቸው፡፡

ኪራይ የሚቆልሉት ደላሎች ናቸው

ከፍና ዝቅ ያለውን የአዲስ አበባ የኑሮ ቅኝት እንዲህ የሚመሰክሩት የአዲስ አበባ የኪራይ ቤቶች፣ በመካከሉ ላለው ነዋሪ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና የሚፈጥሩ ሆነው ይገኛሉ፡፡ በአዲስ አበባ ሌላው ጥልቅ ችግር ለመሆኑ በመንግሥትም በሕዝቡም ስምምነት የሚደረግበት ትልቅ ችግር የደላሎች ሚና ነው፡፡ የአዲስ አበባ አስተዳደር በተለያዩ አጋጣሚዎች የደላሎችን ተግባር በማስመልከት ከፍተኛ ቅሬታ ሲያሰማ ማድመጥ የተለመደ ነው፡፡ ከጥቂት ወራት በፊት ስለብርቱካን ዋጋ መወደድ ለማሳሰብ በተጠራው የንግድ ሚኒስቴር ስብሰባ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ደላሎች ከሚችለው በላይ ሆነውበት መቸገሩን አስታውቋል፡፡

ጥቂት ቢቆይም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን፣ ‹‹ጉዳይ እናስፈጽማለን›› በሚሉ ደላሎች መቸገሩን አስታውቆ ነበር፡፡ ዋናው መሥሪያ ቤት ድረስ ሰተት ብሎ የረዘመው የደላሎች እጅ፣ በተለይ ከሦስት ዓመት በፊት ጡዘት ላይ ደርሶ የነበረውን የአነስተኛ ግብር ከፋዮች ጉዳይ መነሻ በማድረግ በባለሥልጣኑ ጉዳያቸውን ሊያይ የሚችል አካል እንደሚያውቁና እንደሚያስጨርሱላቸውና ውክልና ሳይቀር እንዳላቸው በመግለጽ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ሳይቀር ማስቸገራቸው ሲነገር ቆይቷል፡፡

ይህ መሆኑ ደግሞ በየትኛውም የአዲስ አበባ ከተማ ጉዳይ ላይ ደላሎች አይነኬና የማይፈነቀል ሚና ይዘው ለመቆየታቸው ምክንያት ሆኗል፡፡ ከቤት ሠራተኛ ቅጥር ጀምሮ በቤት ሽያጭና ግዥ፣ አሁን በግልጽ አይሁን እንጂ በድብቅ የመሬት ሽያጭና ግዥ በማካሄድ፣ ከውጭ ዕቃ በማስመጣትና ደንበኛ በማፈላለግ ላይና በየትኛውም የኢኮኖሚ አውታር ላይ የደላሎች ሚና ከደም ሥር በላይ ሆኖ ይታያል፡፡

በቤት ኪራይ ላይ የሚታየው የደላሎች ጣልቃ ገብነት ደግሞ አብዛኛውን የከተማ ነዋሪ ከማንገሽገሽ አልፎ አንዳንዶችን ለጠብ ሲጋብዝ ማየት እየተለመደ ነው፡፡ በኮንዶሚኒየም ቤቶች ለሚከናወኑ የኪራይ ድርድሮች ደላሎች ማዕከላዊውን ቦታ ይይዛሉ፡፡ ያለደላሎች ጣልቃ ገብነት የትኛውም ቤት አይከራይም፣ አይሸጥም ሲባል መስማት የተለመደ ነው፡፡ በመካኒሳ ባቱ አራት ባለሁለት መኝታ ቤት ለመከራየት ፈልጋ ዘበኞችን የጠየቀችው እመቤት ጌታቸው የተባለች ወጣት፣ አከራዩን በስልክም በአካልም ማግኘት እንደማትችል ይልቁንም የቤቱን ቁልፍ ከያዘው ደላላ ጋር ተነጋግራ ከተስማማች መከራየት እንደምትችል እንደተነገራት ለሪፖርተር ገልጻለች፡፡

በገዥና ሻጭ መካከል በቀጥታ የሚደረጉ ስምምነቶችን በዚህ ምክንያት ማድረግ አደጋች ሆኖ ይታያል፡፡ አንዳንድ የኮንዶሚኒየም ኮሚቴዎች ግን ይህንን አጥር በመስበር፣ በአከራይና ተከራይ መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት እንዲኖር ለማድረግ ሲጣጣሩ ይታያሉ፡፡ ደላሎች ለአከራዩ የቅድሚያ ክፍያ ለአንድ ዓመት፣ ለስድስት ወር አለያም ለሦስት ወር የሚደረጉ የኪራይ ክፍያዎች ላይ ከሦስት እስከ አምስት በመቶ የአገልግሎት በማስከፈል እንደሚያከራዩ ሲገለጽ፣ ደላሎች በባለቤት ስም ሆነው ለሚያከራዩት ቤት እስከ አሥር በመቶ እንደሚያስከፍሉም ይታወቃል፡፡

የቤት ኪራይ ዋጋን በሚመለከት በአሜሪካ እንደሚሠራው ዓይነት ጥናት በኢትዮጵያ ይፋ ሲደረጉ ባይታም፣ ለአገሪቱ የዋጋ ንረትና ግሽበት አስተዋጽኦ እንዳለው የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ በየወሩ ይፋ የሚያደርገው የሸማቾች ዋጋ መመዘኛ አሃዝ ያመለክታል፡፡ የስታቲስቲክስ ኤጀንሲ የሸማቾች ዋጋ መመዘኛ ኢንዴክስ (ሸማቾች ለተወሰኑ ዕቃዎችና አገልግሎቶች የከፈሉትን አማካይ የዋጋ ለውጥ ለመለካት የሚያገልገግል ጠቋሚ አሃዝ ነው ሲል ኤጀንሲው ይገልጸዋል) ሲተነትን፣ ምግብ ነክ የሆኑና ምግብ ነክ ያልሆኑ የሸማቾች ዋጋ መመዘኛ ኢንዴክስ ብሎ ባስቀመጣቸው መለኪያዎች መሠረት፣ ምግብ ነክ ካልሆኑት መመዘኛ አሃዞች መካከል፣ የሸማቾች የችርቻሮ መመዘኛ ዋጋን በዘንድሮውና በዓምናው መካከል ያለውን ልዩነት በማነፃፀር ያቀርባል፡፡ በዚህ መሠረት ከቤት መሥሪያ ዕቃዎች፣ ከውኃና ኢነርጂ ወጪዎች ጋር የተደለደለው የቤት ኪራይ አንድ ላይ 7.8 ከመቶ ጭማሪ በማሳየት፣ ባለፈው ዓመት ኅዳር ወር ላይ ከነበረው አገር አቀፍ ጠቅላላ የችርቻሮ ኢንዴክስ ጋር ሲነፃፀር የ7.9 ከመቶ ጭምሪ እንዲሳይ ምክንያት ለመሆን መቻሉን የስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ይፋ አድርጓል፡፡ እስካሁን ባለው አካሄድም የቤት ኪራይ ወጪ ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አልታየም፡፡ ሆኖም ይህ ጠቋሚ አሃዝ የቤት ኪራይ ዋጋን በተናጠል ካለማመልከቱም በላይ፣ ምን ያህል የቤት ተከራዮች እንዳሉ (የመኖሪያና የሥራ ቦታ) አያሳይም፡፡ ምን ያህል ተጨማሪ ተከራይ ሊኖር እንደሚችል፣ የኪራይ ዋጋ በቀጣዩ ወር ወይም ዓመት ምን ያህል ሊሆን እንደሚችል ወዘተ. ያለውን ትንታኔም የሸማቾች ዋጋ መመዘኛው አይጠቁምም፡፡


Sport: “ኢትዮጵያን አሸንፈን ለዓለም ዋንጫ በማለፋችን የቼልሲ ተጨዋቾች ደስታቸውን ገልፀውልኛል›› –ኬኔት ኦሜሮ (Kenneth Omeruo)

$
0
0

ናይጄሪያ የዓለም ዋንጫ ህልሟን እውን ለማድረግ ኢትዮጵያን ማሸነፍ ነበረባት፡፡ አዲስ አበባ ላይ 2-1 ድል ካደረገች በኋላ በካላባር ከተማም በሌላ ድል ቲኬቷን ቆረጠች፡፡ ኬኔት ኦሜሮ ከፈንጠዚያው በኋላ ወደ ቼልሲ ሲመለስ ዴቪድ ሉዊዝ ጨብጦት ‹‹ወደ ብራዚል እንኳን ደህና መጣችሁ›› ብሎታል፡፡ ሉዊስ በሀገሩ የሚስተናገደውን ውድድር አስመልክቶ ያበረታታው ወጣት በቼልሲ ተሰላፊነትን አያግኝ እንጂ የስታምፎርድ ብሪጁ ክለብ ንብረት ነው፡፡ በሰማያዊዎቹ ክለብ ውስጥ የሚገኙት የሉዊዝ ሀገር ልጆች ኦስካር፣ ራሚሬዝና ዊልያንም የ20 ዓመቱን የመሀል ተከላካይ ‹‹እንኳን ደስ ያለህ›› ብለውታል፡፡ ከዚያም ሌሎቹም ተጨዋቾች እየተፈራረቁ ቀጥለዋል፡፡

omerou2

ኦሜሮ በቼልሲ ገና የመጀመሪያ ጨዋታውን እንኳን አላደረገም፡፡ ሆኖም በተጨዋቾች ዘንድ ይወደዳል፡፡ 59 ቁጥር ማሊያ ያደርጋል፡፡ በጆዜ ሞውሪንሆም የዋናውን ቡድን ማሊያ እንዲሰጠው ተደርጓል፡፡ ተስፋም ጥለውበታል፡፡ ስለዚህ ከሙሉ ቡድኑ ጋር አብሮ ልምምድ ይሰራል፡፡
በ2014ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ከወጣት ከዋክብት መካከል ኦሜሮ እንደሚካተትበት ከወዲሁ ግምት ተሰጥቶታል፡፡ ይህ ዓመትም በጥሩ ሁኔታ አልፎለታል፡፡ ናይጄሪያ ከኬፕቬርዴ ጋር ባደረገችው ጨዋታ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሀገሩ ብሔራዊ ቡድን ተሰልፏል፡፡ በብራዚል የኮንፌዴረሽን ዋንጫ ላይ ተሳትፏል፡፡ ለ15ኛ ጊዜ ለንስሮቹ ባደረገው የካላባር ጨዋታም ሃገሩን ለዓለም ዋንጫ ለማሳለፍ በቅቷል፡፡
‹‹በዓለም ዋንጫ ላይ ለመጫወት ስመኝ ኖሬያለሁ›› ኦሜሮ ይናገራል፡፡ ‹‹በኮንፌዴሬሽንስ ካፕ ላይ መሳተፋችን ዓለም ዋንጫ ላይ የመቅረብ ፍላጎታችንን ጨምሮልናል፡፡ አሁንም የምድብ ድልድሉን በጉጉት እጠባበቃለሁ፡፡
‹‹በቼልሲ ብቻ ትኩረታችንን በክለባችን ላይ አድርገን እንሰራለን፡፡ አንዳንድ ጊዜ ጆዜ ያስቀናል፡፡ ባለፈው ሳምንት አንድ የልምምድ ፕሮራም ላይ አንድ ኳስ ላቀብል ብዬ ተበላሸብኝ፡፡ ጆዜም እንዲህ አለኝ፡፡ ‹‹በዓለም ዋንጫ ላይ እንዲህ ካደረግክ ናይጄሪያ ከውድድሩ ትወጣለች›› ሁላችንም ሳቅን፡፡ አሁን ስለ ዓለም ዋንጫ በተጨዋቾች መካከል ምንም ነገር የለም፡፡ ያለው ዝምታ ብቻ ነው፡፡ ከዕጣው ድልድል በኋላ ግን ጫጫታ ይኖራል፡፡
‹‹ስለዓለም ዋንጫው ከሉዊዝ ጋር አውርተናል፡፡ ጥሩ እንግሊዝኛ ያወራል፡፡ በእውነቱ መልካም ሰው ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር ልንጫወት ስንሄድ ሉዊዝ ‹‹እውን አሁን ለዓም ዋንጫ ልታልፉ ነው›› እያለ ሲያሾፍብን ነበር፡፡ አሸንፈን ስንመለስ ግን ሁሉ ደስታቸውን ገልፀውልናል፡፡ ሉዊዝም ‹‹ጥሩ ሰርታችኋል፣ እንኳን ወደ ብራዚል ደህና መጣችሁ›› ብሎ ተቀብሎናል፡፡
‹‹ለዓለም ዋንጫ ማለፍ ትልቅ ነገር ነው፡፡ ሁሉም በጣም ደስተኛ ሆኗል፡፡ ልክ የአፍሪካ ዋንጫን እንዳነሳንበት ጊዜ አይነት ነው፡፡ ህዝብ ወደ ጎዳናዎች ወጥቷል፡፡ ደጋፊዎቻችንን ቅር አላሰኘንም፡፡ ለእነርሱ ሲባል ማለፍ ነበረብን፡፡ (በኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ላይ ከስፔን ጋር ስንጫወት የትከሻ) ጉዳት በደረሰብኝ ጊዜ ከደጋፊዎች መልዕክቶችና ትዊቶች ይደርሱኝ ነበረ፡፡ እኔን ለማየት ምን ያህል እንደናፈቁ ይገልፁልኛል፡፡ አሰልጣኝ ስቴፋን ኬሺም በምን አይነት ጤንነት ላይ እንዳለሁ እየደወለ ይጠይቀኝ ነበር፡፡ አሁንም የቡድኑ አባል መሆኔን ይነግረኛል፡፡ ስለዚህ በድጋሚ ለመጫወት ጓጉቼ ነበር››
ለንስሮቹ የዘንድሮ አምስተኛው የዓለም ዋንጫ ነው፡፡ 160 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ሀገር ቡድኗን በታላቅ ስሜት ትደግፋለች፡፡ ‹‹ልጅ ሳለሁ ናይጄሪያ ስታሸንፍ ባደግኩባት ዋና ከተማ አቡጃ ህዝቡ አደባባይ ወጥቶ ደስታውን ሲገልፅ እኔም ተቀላቅያቸው ነበር፡፡ አባቴ የቧንቧ ሰራተኛ ነው፡፡ እናቴ ደግሞ ትንሽ ሬስቶራንት አላት፡፡ የናይጄሪያ ጨዋታዎች ሁልጊዜ እንከታተል ነበር፡፡
‹‹ገና ልጅ ሳለሁ አንድ ቀን የናይጄሪያን ብሔራዊ ቡድን ማሊያ መልበሴ እንደማይቀር እናቴ ትነግረኝ ነበር፡፡ እንዳለችውም ሆነ፡፡ በ2009 የዓለም ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ በአቡጃ ተዘጋጅቶ ነበረ፡፡ ያም እናቴን በጣም አስደስቷታል፡፡ ምንም ያመለጣት ነገር የለም፡፡ ሬስቶራንቷን ሳይቀር ዘግታ ወደ ስታዲየም መጥታለች፡፡ ሁልጊዜም መልካም ዕድል እንዲገጥመኝ ትመኛለች››
በ1994 ናይጄሪያ በዓለም ዋንጫ የመጨረሻ 16 ቡድኖች አንዷ ስትሆንና በፈረንሳይ የዓለም ዋንጫ (ኢትዮጵያን… ወደ ገጽ 23 የዞረ)

 

ስትሳተፍ ኦማር ጨቅላ ህፃን ስለነበር አያስታውስም፡፡ ‹‹ሰዎች ሁልጊዜ ስለ 1994ቱ ቡድን ያወራሉ፡፡ ማይክል አሜናሎ (የአሁኑ የቼልሲ የቴክኒክ ዳይሬክተር) የቡድኑ አባል ነበር፡፡ የአሁኑ የንስሮቹ አሰልጣኝ ኬሺ ደግሞ የቡድኑ አምበል ነበር፡፡ ‹‹ሲመክረን በአሁኑ ቡድን ውስጥ ከ1994ቱ ቡድኑ ጋር የሚመሳሰል መንፈስ እንደሚመለከት ይነግረናል፡፡ ይህ ደግሞ ለእኛ ብዙ ትርጉም አለው›› አሚሮ ለ1994ቱ የአፍሪካ ሻምፒዮን ያለውን ክብር ይገልፃል፡፡
‹‹በብሔራዊ ቡድኑ ውስጥ አንድነት የሌለባቸው ጊዜያት ነበሩ፡፡ በ2010 በውጤቱ ሃገሪቷ አዝና ነበር፡፡ ፕሬዝዳንቱ ጉድላክ ጆናታን ቡድኑ በደቡብ አፍሪካ ባሳየው ብቃት በጣም ከመቆጣታቸው የተነሳ ለተወሰነ ጊዜ አግደውት ነበር፡፡ አሁን ግን በቡድኑ ዙሪያ ያለው ነገር ሁሉ በጣም ጥሩ ነው፡፡ በህብረት እንሰራለን፡፡ ብትመለከተን ሁሉም እርስ በርሱ ቀልድ ሲለዋወጥ ታያለህ፡፡ በቡድናችን ውስጥ አዙቢኬ ኤግዌክዌ የተባለ ቀልድ ወዳጅ ተጨዋች አለ፡፡ በናይጄሪያ ለዋሪ ዋልቭስ ክለብ የሚጫወተው የመሀል ተከላካይ ነው፡፡ ካልጮኸ አያወራም፣ በጣም ቀልደኛ ነው፡፡ አሰልጣኛችንን እንኳን ሳይቀር ያስቃቸዋል፡፡ የአፍሪካ ዋንጫን አሸንፈናል፡፡ በኖቬምበር የዓለም ከ17 ዓመት በታች ዋንቻ አንስተናል፡፡ እንደገናም ለብራዚሉ የዓለም ዋንጫ አልፈናል፡፡ በዓለም ዋንጫ ላይ ደግሞ ተደናቂ ነገር ማሳየት አለብን›› ይላል፡፡
ኦሜሮ እዚህ ደረጃ ላይ የደረሰው በቀላሉ አይደለም፡፡ ከአቡጃ ጎዳናዎች ተነስቶ ብዙ ለፍቷል፡፡ ‹‹የአቡጃ ልጅ ነኝ፡፡ ያደግኩት እግርኳስን በሚያፈቅር ቤተሰብ ውስጥ ነው፡፡ አባቴ ግብ ጠባቂ ነበር፡፡ በከፍተኛ ደረጃ አልተጫወተም እንጂ ታላቅ ወንድሜም እንዲሁ ይጫወታል፡፡ ታናሼ ለሙከራ ስታንዳርድ ሉዬዥ ይሄዳል፡፡ የአንድ ክለብ አሰልጣኝ ወደ ቤታችን መጥቶ ከወላጆቼ ጋር ተነጋገረ፡፡ ልጃችሁ ከእኔ ጋር ይጫወታል አላቸው፡፡ ዕድሜዬ 10 ዓመት እስኪሞላኝ ድረስ በባዶ እግሬ ተጫውቻለሁ፡፡ በ2009 ለሁለት ወራት ሙከራ ወደ አንደርሌክት ሄጄ ተመለስኩ፡፡ ከዚያም ስታንዳርድ ሊዬዥ ላከልኝ፡፡ ለሊዬዥ ተጠባባቂ ቡድን ውስጥ መጫወት ጀመርኩ፡፡ ከዚያም ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ላይ ቀረብኩ፡፡ ቼልሲም ሊያስፈርመኝ ፍላጎት አሳየኝ፡፡ የጠራኝ ኤሚላኖ ነበር፡፡ ላምን አልቻልኩም፡፡ ያደግኩት ቼልሲን እያየሁ ነው፡፡ ሚኬልን እወደዋለሁ፡፡ ስለሴሌስቲን ባባደሮም እሰማ ነበር፡፡ ቼልሲ ሲያሸንፍ በናይጄሪያ ልክ የሀገራቸው ቡድን ያሸነፈ ያህል ይጨፍራሉ፡፡ በናይጄሪያ ከማንቸስተር ዩናይትድ የበለጠ ቼልሲ ብዙ ደጋፊ አለው፡፡ ዩናይትድ በሁለተኛ ደረጃ ይጠቀሳል፡፡
‹‹ቼልሲን ማንቸስተር ዩናይትድ ሲጫወቱ በአንዳንድ ቦታዎች ሁከትና ጥል ይነሳል፡፡ በከተማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ የሚሉ ብስክሌተኞች የቼልሲን ወይም የማንቸስተር ዩናይትድን አርማ የውለበልባሉ፡፡ በናይጄሪያ እግርኳስ ይህን ያህል ይወደዳል፡፡
‹‹ቼልሲ እንዳስፈረመኝ ሳይውል ሳያድር ለዴን ሃግ ክለብ በውሰት ሰጠኝ፡፡ ብቃቴን እንዳሻሽል ተብሎ ነው፡፡ ደጋፊዎቻቸው በጣም ስሜታዊ ናቸው፡፡ ለእያንዳንዱ ተጨዋች ብቃቱን እንዲያሳድግ በደጋፊዎች በግል መዝሙር ይወጣለታል፡፡ የዴንሃግ ክለብ ደጋፊዎች ስሜት እየጠሩ ዘምረዋል፡፡
‹‹እዚህ ነው፣ እዚያ ነው፡፡ ሁሉ ቦታ ነው እያ ይዘምሩልኝ ነበር››
አሜሮ የተጎዱ ተጨዋቾችን ለመተካት ሲባል በቀኝ መስመር ተከላካይነት ተጫውቷል፡፡ ሆኖም ‹‹ምርጡ ቦታዬ የመሀል ተከላካይ ቦታ ነው›› ይላል፡፡ አሰልጣኝ ሞውሪንሆም በትክክል መዝነውታል፡፡ ‹‹(ሞውሪንሆን) ጓደኛዬ ኬኔት›› እያለ ይጠራኛል፡፡ ስለ እኔ የሚያወራበት መንገድ ሁሉ ደስ ይላል፡፡ ከአፍሪካ ዋንጫ በኋላ እንደፈለገኝ ሚኬል ነግሮኛል፡፡ ስላወቀኝ በጣም ተደሰትኩኝ፡፡
‹‹በናይጄሪያ ሁሉም ሰው ልጅ ሰው ይለዋል፡፡ ስትቀርበው ደግሞ ልዩ ሰው መሆኑን ትረዳለህ፡፡ ተጫዋቾች ያከብሩታል፡፡ ተጨዋቾችን እንዴት መያዝ እንዳለበት ያውቅበታል፡፡ ከእኛ ጋር እንዴት መነጋገር እንደሚገባውም ይረዳል፡፡ ልምምዱ ምርጥ ነው፡፡ በመጀመሪያ ለመልመድ ተቸግሬ ነበር፡፡ ከዌስትሃም ጨዋታ በፊት ተጋጣሚያችን በምን አይነት ዘዴ እንደሚጫወት ያውቃል፡፡ ጆዜ በልምምድ ሜዳ ላይ የሚናገረው ሁሉ በጨዋታ ላይ ሲሆን ታየዋለህ፡፡ በዚህ ምክንያት የበለጠ አክብሬዋለሁ፡፡
‹‹ተጨዋቾች ጥሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ማይክል ኤሲዬን ለእኔ መልካም ነው፡፡ አሽሊኮል ሁልጊዜም ያበረታታኛል፡፡ ትክክለኛ ሸርተቴ በወረድኩ ቁጥር የእርሱን የማበረታቻ ድምፅ ትሰማለህ፡፡ አይዞህ ኬኔት ይለኛል፡፡ ጊዜህ ይመጣል፡፡ ሩቅ አይደለም፡፡ ዕድል ስታገኝ ተጠቀምበት እያለ ይመክረኛል፡፡ ጆን ቴሪም እንዲሁ ጥሩ ሰው ነው፡፡ ያወያየናል፡፡ ግዙፍና ጠንካራ ነው፡፡ እንደ ወጣት ተጨዋችነቴ አንጋፎቹ በልምምድ ላይ ብዙ ሲሰሩ ስመለከት ለራሴ ብዙ መስራት እንዳለብኝ እነግረዋለሁ፡፡
‹‹በልምምድ ላይ በትኩረት ተግቼ መስራት አለብኝ፡፡ እያንዳንዱ አጥቂ የየራሱ ተሰጥኦ አለው፡፡ ለአምስት ደቂቃዎች ጎል ካልተቆጠረብህ በየትም ቦታ ብጫወት እችላለሁ ብለህ ታምናለህ፡፡ ከፈርናንዶ ቶሬዝ ጋር በተቃራኒ ሆነህ መጫወት ይከብዳል፡፡ ጠንካራ መሆን አለብህም፡፡ እንዳያልፍህ መጠንቀቅ ይገባሃል፡፡ እነዚህ በቤልጂየም ሳለሁ ስከታተላቸው የነበሩ ታላቅ ተጨዋቾች ናቸው፡፡ ከእነርሱ ጋር መጫወት ያስደስታል፡፡ ሳሙኤል ኤቶ በአፍሪካ ትልቅ ተጨዋቾች ነው፡፡ ኤቶንና ኤሲዬንን ማግኘት በመቻሌ በጣም ደስተኛ ሆኛለሁ›› እያለ ኦሜሮ በቼልሲ ህልሙን እየኖረ መሆኑን ያስረዳል፡፡ ህልሙ ግን በዚህ አያበቃም፡፡ ከፕሪሚየር ሊጉ ታላላቅ ክለቦች በአንዱ ውስጥ በቋሚነት መጫወት ደግሞ ቀጣይ ምኞቱ እንደሚሆን ጥርጥር አይኖርም፡፡

 

Health: 9ኙ ቦርጭን ማጥፊያ የምግብ ዓይነቶች

$
0
0

(ይህ ጽሁፍ በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 58 የታተመ ነው።)
ሆድ አካባቢ የሚገኝን የስብ መጠን(ቦርጭን) ለመቀነስ ሙከራ ሲያደርጉ የፕሮቲን ይዘታቸው ከፍ ያለ፣ ሰውነት ውስጥ ተቋጥሮ የሚገኝን አላስፈላጊ ውሃ ማስወገድ የሚችሉ እና የምግብ መፈጨት ሂደትን የሚያቀላጥፉ ምግቦችን መርጦ አዘውትሮ መመገብ ይመከራል፡፡ እነዚህ ምግቦች የምግብ መፈጨት ሂደትን ቀልጣፋ ከማድረግ ባሻገር ሆድ አካባቢ የሚገኝን አይነተኛ ሚና ይጫወታሉ፡፡
ቦርጭን (ሆድ አካባቢ የሚገኝን የስብ መጠን) ሊቀንሱ የሚችሉ የምግብ አይነቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
color-133-Tomato-2
ቲማቲም

ቲማቲም ስብን ለማቃጠል ከሚረዱ ምግቦች ውስጥ አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ቲማቲም የማይነጥፍ ‹‹Anti oxidants›› በአጭሩ ኦክሲጅን ከሌሎች ‹ፍሪ ራዲካልስ› ከሚባሉ ንጥረ ነገሮች ጋር ውህደት በመፈፀም ሰውነት ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳይ ይከላከላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቲማቲም ‹ሌፕቲን› የተሰኘ ፕሮቲን ሰውነታችን ውስጥ በብዛት እንዲመረት ስለሚያግዝ የምግብ ፍላጎትን ይጨምራል፡፡ እንዲሁም የምግብ መፈጨት ሂደትን ቀልጣፋ ያደርጋል፡፡
ሀባብ

ሀባብ የውሃ ሀብታም ነው፡፡ 94% የሚደርሰው ይዘቱ ውሃ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ተመራጭ አነስተኛ ካሎሪ ያለው ፍራፍሬ ነው፡፡ ሆድ አካባቢ የሚገኝን አላስፈላጊ ፈሳሽ በማስወገድ የሆድ መጠን እንዲስተካከል ያደርጋል፡፡ ሆድ አካባቢብቻ ሳይሆን ሌሎች የሰውነት ክፍሎ ውስጥ ውሃ አለአግባብ እንዳይጠራቀም ያደርጋል፡፡
እንጉዳይ

እንጉዳይ የ‹ፋይበር› ይዘቱ ከፍተኛ ስለሆነ ረዘም ላለ ጊዜ ጥጋብ እንዲሰማችሁ በማድረግ የምግብ ፍላጎታችሁን እና አወሳሰዳችሁን ይቀንሳል፡፡ የምግብ መንሸራሸር ሂደትንም ያቀላጥፋል፡፡
papaya
ፓፓያ
ፓፓያ ሆድ አካባቢ የሚገኝን ስብ ለማቃጠል በእጅጉ ይረዳል፡፡ ‹ፓፔይን› የሚባል ኢንዛይም ውስጡ ስለሚይዝ ይህ ኢንዛይም ደግሞ ምግብ በፍጥነት እንዲሰባበር እና ሆድ ልሙጥ እንዲሆን ያግዛል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ፓፓያ አላስፈላጊ እብጠት እና መነፋትን ያስተካክላል፤ የምግብ መፈጨት ሂደትንም ቀልጣፋ ያደርጋል፡፡
ኦሊቭ ኦይል
ብዙዎቻችን ክብደት ለመቀነስ ሙከራ ስናደርግ ከስብ ነክ ነገሮች እንድንርቅ ተመክረናል፡፡ ነገር ግን ኦሊቭ ኦይል ውስጥ የሚገኘው ኦሌይክ አሲድ ደማችን ውስጥ የሚገኝን የስኳር መጠን በመቆጣጠር ለክብደት መቀነስ ቀላል የማይባል አስተዋፅኦ ያበረክታል፡፡
አልሞንድስ
አልሞንድስ የካሎሪ ይዘታቸው ከፍተኛ ቢሆንም ሆድ አካባቢ ውፍረት በመፍጠር ግን አይታሙም፡፡ ይልቁንም ለቆዳ ጤንነት መጠበቅ እገዛ ሊያደርግ የሚችል ቫይታሚን ሲ ውስጣቸው ይገኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የፋይበር ይዘታቸው ከፍተኛ በመሆኑ የምግብ ፍላጎትን ያስተካክላሉ፤ የምግብ መፈጨት ሂደትን ያፋጥናሉ፡፡ ይህ በበኩሉ ሰውነታችን ውስጥ የሚገኝን አላስፈላጊ ስብ በማቃጠልና በማቅለጥ ክብደት እንድንቀንስ ያግዛል፡፡
banana
ሙዝ
ክብደት ለመቀነስ ሙከራ ስናደርግ ብዙዎቻችን ሙዝ መመገብ እናቆማለን፡፡ ይሁን እንጂ ሙዝ የፖታሺየም ይዘቱ ጥሩ በመሆኑ ሰውነት ያለአግባብ የሚቋጥረውን የውሃ መጠን ይቀንሳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሙዝ በፋይበር የበለፀገ ስለሆነ የምግብ ፍላጎታችሁ ያለአግባብ ሳይጨምር ጤናማ ሆኖ እንዲቆይ እገዛ ያደርጋል፡፡
አፕል
አፕል መርዛማ ነገሮችን የማስወገድ ባህሪ አለው፡፡ በዚህ ምክንያት የምግብ መፈጨት ሂደትን ቀልጣፋ ያደርጋል፤ ሰውነታችን ውስጥ የሚገኝ አላስፈላጊ ውሃም እንዲወገድ ያደርጋል፡፡
ኦትስ
ኦት የካሎሪ ይዘቱ አነስተኛ ቢሆንም ለሰውነት የሚሰጠው ኃይል ግን ከፍተኛ ነው፡፡ ክብደት መቀነስ ስትፈልጉ ታዲያ ጠዋት ከቤታችሁ ኦትስ ቀማምሳችሁ ብትወጡ በቂ ኃይል ስለሚሰጣችሁ የምግብ ፍላጎታችሁን ጋብ አድርጎ በማዋል ክብደት እንድትቀንሱ ያደርጋል፡፡

ኢትዮጵያ የብሄራዊ እርቅ ኮሚሽን ማቋቋም የሚያስፈልጋት ጊዜ ላይ ናት (ገለታው ዘለቀ)

$
0
0

   ገለታው ዘለቀ  

reconciliatioባለፉት ጥቂት ተከታታይ ጽሁፎች ላይ እንደተወያየነው በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ውስጥ መግባት ኢትዮጵያን እንደገና ለማነጽ ኣማራጭ መፍትሄ ይሆናል። ታዲያ በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ላሉብን ውስብስብ ሁለንተናዊ ችግሮች ሁሉ መፍትሄ ይሆናል ማለት ሳይሆን ቅድሚያ ተሰጥቷቸው ሊፈቱ የሚገባቸውን ባህላዊ ማህበራዊ ችግሮች መስመር በማስያዝ በሂደት እየተፈቱ እንዲሄዱ ከማድረጉም በላይ ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት ደግሞ ቀጥተኛ ያልሆነ ኣስተዋጾ ስላለው ነው።   በችግር ኣፈታት ጊዜ ከሚመጡት መፍትሄዎች መካከል የትኛውን ብናስቀድም ነው ሌላውን ችግርም ኣብሮ ሊፈታልን የሚችለው ብለንም እንጠይቃለንና በዚህ ረገድ በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ውስጥ መግባት ሌሎች መጋቢና ተለጣጣቂ ችግሮችን ለመፍታት ይጠቅማል ከሚል ነው።

ባለፉት ዘመናችን ያሉብንን ሃገራዊ ችግሮች ሁሉ ስንዘረዝር ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ ምናምን እያልን ለያይተን እንዘርዝራቸው እንጂ ሁሉንም ችግሮች ለመፍታት የምንሄድበት መንገድ ግን ፖለቲካዊ ይዘት ባለው መንገድ ነው። ፖለቲካዊ ችግሮቻችንን ፖለቲካዊ ይዘት ባለው መንገድ፣ ማህበራዊውን ደግሞ ማህበራዊ በሆነ መንገድ፣ ኢኮኖሚውንና ሌሎቹንም እንደ ተፈጥሯቸው ከመፍታት ይልቅ ለሁሉም ችግር ፖለቲካን የችግር መፍቻ ቁልፍ ኣድርገን መውሰዳችንና የፖለቲካው ጣልቃ ገብነት በማየሉ ችግሮቻችን መፍትሄ ሳያገኙ እንዲቆዩ ያደረገ ይመስላል። ለማህበራዊ ችግሮቻችን ሁሉ ፖለቲካዊ ይዘት ያለው መፍትሄ ከማምጣት ይልቅ ባህላዊና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዩችን ከባህርያቸው ኣንጻር ለመፍታት ብንጥር ችግሮቻችን ኣሁን ያሉትን ያህል ኣይበዙም ነበር። በኣሁኑ ሰዓት ፖለቲካው ማህበራዊውን ህይወታችንን የነካበት ምክንያት የማያገባው ውስጥ ገብቶ በመገኘቱ ነው።

በዛሬው ውይይታችን የምናነሳው ጉዳይ በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ስንል ኣንድ ቁልፍ ቃል በዚህ የመወያያ ርእስ ውስጥ ይሰመርበታል። ይህም  ስምምነት የሚለው ነው። ስምምነት ስንል ወይም እንዴት ኣድርገን ነው ወደ ስምምነት የምንመጣው ስንል  በዚህ ኣገባብ ሶስት ጉዳዩችን ይዳስሳል።

1. ያለፈውን ታሪካችንን እንዴት ኣድርገን ነው ወደ ስምምነት የምንመጣው? ታሪካዊ ግድፈቶችን እንዴት እንፍታቸው? እንዴትስ እንያቸው? በሚለው ዙሪያ ያጠነጥናል::

2. ችግሮቻችን ታሪካዊ ብቻ ሳይሆኑ ኣሁን ድረስ ስላሉ እነዚህን ችግሮች እንዴት እንያቸው?  እንዴትስ እንዳይቀጥሉ ማድረግ እንችላለን? የሚለውን ይይዛል

3. ሁላችን የምንፈልጋትን የወደፊት ኢትዮጵያን እንዴት ኣድርገን ነው በጋራ ጥሩ መሰረት ጥለን መጻኢ እድሏን የምናበጀው? የሚለውንም ይይዛል።

እንግዲህ በነዚህ ከፍ ብለን በዘረዘርናቸው ኣሳቦች ዙሪያ ስምምነት ላይ መድረስ ያስፈልጋል ስንል በምን መንገድ ነው የምንወያየውና የምንስማማው? የትና በማን ኣማካኝነት ይፈጸማል? የሚሉ በጣም ተግባር የናፈቃቸው ጥያቄዎች መነሳታቸው ኣይቀርም። ምክንያቱም ሃገራችን ውስጥ ላሉት ችግሮች የመፍትሄ ኣሳብ ኣይደለም የጠፋው:: በየጊዜው በቡድንም በግልም ጠቃሚና የሃገርን ችግር ሊያቃልል የሚችል ኣሳብ ይመጣል:: ነገር ግን እነዚህን የመፍትሄ ኣሳቦች የሚያደራጅና መልክ የሚያስይዝ ባለመኖሩ እንዲሁ ኣንዱን እያነሳን ኣንዱን እየጣልን እንኖራለን።

በዛሬው ውይይታችን ስምምነት የሚለውን ኣሳብ እንዴት ልናመጣው እንደምንችል ተግባራዊ ሃሳቦችን እናነሳለን። እንግዲህ ወደ ነጥባችን እንውረድና ስምምነትን ልናመጣበት ከምንችልባቸው ዘዴዎች ኣንዱ የብሄራዊ እርቅ ኮሚሽንን ኣቋቁሞ በመስራት ነው። ይህ ኮሚሽን ኣሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ቢደግፈውና ኣብሮ ቢሳተፍ እሰየው ካልሆነም ግን ከመንግስት እውቅና ውጭ መቋቋም ይችላል። መንግስት ደገፈው ኣልደገፈው የሚያመጣው ችግር ኣይኖርም። በዚህ ጉዳይ ላይ ወደ ሁዋላ እንወያያለን። ለኣሁኑ ስለ ብሄራዊ እርቅ መሰረታዊ ጉዳዮችን ኣንስተን እንወያይ።

ስለ ብሄራዊ እርቅ ምንነትና ይዘት እንዲሁም ኣፈጻጸም ስንወያይ ብሄራዊ እርቅን የምናየው  ባለፈው በተወያየንበት በስምምነት ላይ በተመሰረተ የባህል ውህደት ጽንሰ ሃሳብ ማእቀፍ (framework) ውስጥ ነው።

 

የብሄራዊእርቅምንነት ይዘትና ኣፈጻጸም

ከሁሉ ኣስቀድመን ብሄራዊ እርቅ የሚባለው ጽንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ሁኔታ ምን ማለት እንደሆነ ልንበይነው ይገባል። ብሄራዊ እርቅ በኣለማችን ታሪክ ውስጥ በብዙ ኣገሮች የተፈጸመ ሲሆን የእርቁ ትርጓሜና ኣፈጻጸም እንዲሁም ግቦች ሁሉ ሊለያዩ ይችላሉ። እኛ ኢትዮጵያዊያን ወደ ብሄራዊ እርቅ ለመግባት መጀመሪያ ብሄራዊ እርቅ በኢትዮጵያ ሁኔታ (context) ምን ማለት እንደሆነ በሚገባ ካልተረዳን ብሄራዊ እርቁ ግቡን ላይመታ ይችላል። በመሆኑም ብሄራዊ እርቅ ማለት ምን ማለት ነው? የሚለውን ጉዳይ ኣንስተን በሚገባ እንወያይ። ሃሳባችንን ለማፋፋት ብሄራዊ እርቅን ከኣንዳንድ ሃገሮች ታሪክ ኣንጻር በመጀመሪያ እንመልከት። ለምሳሌ  ያህል በኣውስትራሊያ ውስጥ የብሄራዊ እርቅ ጉዳይ ተነስቷል። እንደሚታወቀው ከታላቋ ብሪታኒያ የኣስራ ስምንተኛው ክፍለዘመን ሰፈራ ፕሮግራም በፊት ኣውስትራሊያ በነባር(indiginious) ህዝቦች የተያዘች ኣገር እንደነበረች ይታወቃል። በሰፈራው ጊዜ በነባሮቹ ህዝቦች ላይ የመፈናቀል፣ የማንገላታት ወንጀሎች ተፈጽመዋል። ዛሬ የኣውስትራሊያ መንግስት ያን የተፈጸመ ታሪካዊ  ስህተት ኣመርቅዞ እንዳይቆይ የወሰደው ርምጃ ብሄራዊ እርቅ ማድረግ ሲሆን ከ 1998 ዓ.ም ጀምሮ መንግስት የብሄራዊ እርቅ ወይም (National sorry day) ኣውጆ በየዓመቱ እየታሰበ ይገኛል። የዚህ የይቅርታ ቀን ኣዋጅ የሚያሳየው ነገር ላለፉት ስህተቶች ሃላፊነት የሚወስድ ኣካል መገኘቱንና የነበረውን ግፍ እውቅና መስጠት መቻላቸውን ለወደፊቱም እንደዚያ ኣይነት ግፍ እንዳይፈጸም ዋስትና መስጠታቸውን ነው። የኣውስትራሊያ ችግር እንደኛ በሶስት መንገድ ላይታይ ይችላል። ይቅርታው ግን ለስንት ኣመት እንደሚደረግ ኣይታወቅም። ዋናው ግን በነባሩ ህዝብ ዘንድ የነፍስ ጽዳት ለማምጣት የታሰበ በመሆኑ ብሄራዊ እርቁ ለኣውስትራሊያውያን ከፍተኛ ጠቀሜታ ኣለው። የነበረውን ታሪካዊ ችግር እውቅና ሰጥቶ ይቅርታ ማወጁ የኣውስትራሊያን ህዝብና መንግስት ልበሰፊነትና ኣርቆ ኣሳቢነት ያሳያል። ነባር ህዝቦችም በዚህ የሚረኩ ይመስለኛል። ከዛ ውጭ ኣፈታሪክ እንደሚናገረው ራሳቸው ነባር ህዝቦችም ከሌላ ክፍለ ዓለም መጥተው የሰፈሩ ናቸው። ዋናው ጥያቄያቸው በሰፈራው ወቅት የነበረው ግፍና በደል ሲሆን እነሆ ዛሬ ተባብረው ዴሞክራሲያዊ መንግስት  በመመስረታቸው ታሪክን ወደ ሁዋላ ኣይቶ ለችግሮች እውቅና ለመስጠት ችለዋል።

ደቡብ ኣፍሪካን ደግሞ እንይ። በደቡብ ኣፍሪካም እንደዚሁ ታሪካዊ የሆነ ብሄራዊ እርቅ የተካሄደባት ኣገር ስትሆን ከኣፓርታይድ ኣገዛዝ ለመላቀቅም ሆነ ከተላቀቀች በሁዋላ ደቡብ ኣፍሪካን በከፍተኛ የመንፈስ ልእልና ሲመራ የነበረው የብሄራዊ እርቅ ስሜት ነው። በደቡብ ኣፍሪካ ብሄራዊ እርቅ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና ከተጫወቱት መካከል Nelson Mandela ኣውራ ናቸው። በኔልሰን ማንዴላ የተመራው ደቡብ ኣፍሪካን እንደገና የማነጽ ስራ ሲጀመር ኣገሪቱ ያለፈችበትን መራራ ችግር ለመፍታት የተጠቀመችው ዘዴ በሪስቶሬቲቭ  ጀስቲስ (Restorative justice) እና ቀስ እያለ በሚያድግ ዴሞክራሲ ቁስልን ማከምና የወደፊቷን የሁሉም የምትሆንን ደቡብ ኣፍሪካን መገንባት ይመስላል።

ደቡብ ኣፍሪካ ከኣፓርታይድ እንደተላቀቀች ወደ ሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ (Retributive juctice) ኣተኩራ ቢሆን ምናልባትም ውጤታማ ኣትሆንም ነበር። ዋናው ጉዳይ ግን ደቡብ ኣፍሪካ ውስጥ የኣፓርታይድ ገዢዎች ለነበረው ችግር ሃላፊነት የመውሰድና ብሄራዊ እርቅን በሪስቶሬቲቭ ጀስቲስና በዝግ እያለ በሚያድግ ዴሞክራሲ ለመፍታት ፈቃደኛ በመሆናቸው የጥፋትና የሞት መላእክን ከደቡብ ኣፍሪካ ሊያባርሩት ችለዋል። ታላቁ የብሄራዊ እርቅ መሪ ኔልሰን ማንዴላም በዚህ ረገድ የተጫወቱት ሚና ታሪክ ሁሌ ሲዘክረው ይኖራል።

የሩዋንዳን ጉዳይም እናንሳ። ሩዋንዳ በዚህኛው ክፍለ ዘመን የዓለምን ህዝብ ያስደነገጠ ወንጀልን ካስተናገደች በሁዋላ ወንጀሉ ጋብ ሲል የወደፊት ኣቅጣጫዋ ግራ ያጋባት ኣገር ነበረች። ለኣንድ መቶ ቀናት በየቀኑ ስምንት ሺህ ሰዎች፣ በየሰዓቱ ከሶስ መቶ ሰላሳ ሰዎች በላይ ያለቁባት ሃገር የወደፊት እጣ ፈንታዋን ለማሰብ በርግጥም እጅግ ከባድ ስራ ነበር።  በርግጥ ሩዋንዳ ያ ወንጀል ጋብ ሲል ለወደፊት እጣፈንታዋ ወዲያው ኣዋጭ መስመር መስሎ የታያት ብሄራዊ እርቅ ማውረድ ቢሆንም ብሄራዊ እርቁ በሩዋንዳ ሁኔታ ምን መልክ ይያዝ? በምን መልኩ ይፈጸም? የሚሉት ጥያቄዎች ግን በጣም ሊከብዷት የሚችሉ ጉዳዩች ነበሩ። በኣንዳንዶች ዘንድ ኣጥብቆ ይቀነቀን የነበረው ጉዳይ ብሄራዊ እርቁ በሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ ኣማካኝነት ሊፈጸም ይገባዋል የሚል ነበር። ሁላችን እንደምናውቀው ሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ ማለት ለወንጀለኛው ተገቢውን ቅጣት በመስጠት የተበዳይን ነፍስ ማጽዳት ወይም ማርካት ማለት ሲሆን ሪስቶሬቲቭ ጀስቲስ ደግሞ የሚያተኩረው ወንጀለኛውን በመቅጣት ላይ ሳይሆን ተበዳዩን በመካስ ላይ ያተኮረ የፍትህና የእርቅ ማውረጃ ዘዴ ነው። ታዲያ ኣንዳንድ  ሩዋንዳዊያን ሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ ነው ፈውስ የሚያመጣልን ሲሉ በርግጥ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ሳያገኙ ኣልቀሩም። ምክንያቱም ወንጀሉ የተፈጸመው በኣጭር ጊዜ በመሆኑ፣ ወንጀሉ ግድያ በመሆኑ፣ ገዳይና የሟች ቤተሰብ ጎረቤት በመሆናቸው፣ ኣሰቃቂ ወንጀል በመሆኑ ሪትሪቢዮቲቭ ጀስቲስ ተገቢነው እንዲሉ የገፋፋቸው ይመስላል። ይሁን እንጂ በኣንድ መቶ ቀናት ላለቀው ስምንት መቶ ሺህ ህዝብ ገዳዩችና ለገዳዩቹ ተባባሪዎች ፍርድ ለመስጠት ሩዋንዳ ኣቅም ኣልነበራትም። ሩዋንዳ በዚያን ወቅት ላለቁት ስምንት መቶ ሺህ ቱትሲዎችና ለዘብተኞች ወደ ኣንድ መቶ ሺህ ወንጀለኞችን ለፍርድ ኣቅርባ መቅጣት ከፈለገች ኣጠቃላይ የፍርዱ ሂደት ወደ  ኣንድ መቶ ኣመት ይፈጅባት ነበር የሚሉ ወገኖች ኣሉ።  ሪስቶረቲቭ ጀስቲስን ተጠቅማ ችግሯን ለመፍታት ብትሞክር ደግሞ ገዳይና ሟች ጎረቤታም በመሆናቸው፣ የሟች ደም ገና ስላልደረቀ በርግጥ የሃገሪቱ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ሌላ ችግር ውስጥ መውደቁ ሌላ ኣሳብን ያመጣባት ትመስላለች። ሩዋንዳ የነበረችበት መስቀለኛ መንገድ ኣስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የጣላት በመሆኑ ሁለቱንም የፍትህ ኣሰጣጥ ዘዴዎች ኣደባልቃ እንድትሄድ ሳያስገድዳት ኣልቀረም። በመሆኑም ባህላዊ የጋካካ ፍርድ ቤቶችን በማቋቋም የተወሰነውን ችግር በዚህ በሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ የተወሰነውን ደግሞ ዝግ እያለ በሚያድግ ዴሞክራሲና በሪስቶሬቲቭ ጀስቲስ ይፈታል እያለች እየደለለች ማርገብ ችላለች። ከሁሉ በላይ ግን ሩዋንዳ ወደ ዘጠና በመቶ የሚሆነው ህዝብ ክርስቲያን በመሆኑና ኣብያተ ክርስቲያናት የሚሰብኩት የይቅርታና የምህረት ትምህርት የሩዋንዳን ችግር በሪስቶሬቲቭ ፍትህ ለመፍታት ከፍተኛ ኣስተዋጾ ሳያደርግ ኣልቀረም። በኣጠቃላይ የሩዋንዳ ችግር ውስብስብና ኣስቸጋሪ በመሆኑ ሁለቱም የፍትህ ኣሰጣጥ ዘዴዎች ተግባር ላይ የዋሉ ይመስላሉ።

ለኣብነት በየሃገሩ የተፈጸመውን ወንጀል እያነሳን የተወያየነው ችግር በየቤቱ ኣለ፣ ይሁን እንጂ ሁሉም ሃገር ችግሩን ለመፍታት ጥረት እያደረገ ነው ኣገር የቆመው ለማለት ነው። ወደኛው ኣገር እንመለስና ብሄራዊ እርቅ በኢትዮጵያ ምን ማለት እንደሆነ እንመልከት።

በኢትዮጵያ ውስጥ ሊኖር የሚችለውን የብሄራዊ እርቅ ይዘት ለማየት መጀመሪያ ስለ ኣለፈው ታሪካዊ ግድፈቶች ማንሳት ተገቢ ነው። ከፍ ሲል እንዳልነው በኣውስትራሊያ ውስጥ ለነበረው ግፍ ሃላፊነት የሚወስድ እውቅና የሚሰጥ ኣካል ተገኝቱዋል። ወደኛ ሃገር ስንመጣ ላለፉት በደሎች እውቅና ለመስጠትም ሆነ ኣንድ ኣካል ለጥፋቱ ሃላፊነት ለመውሰድ የምንችልበት ሁኔታ ጠፍቷል። ይህ የሆነበት ምክንያት ሁሉም የባህል ቡድን በየፊናው ባለፉት ስርዓቶች ተጎድቻለሁ ባይ በመሆኑ ነው።

በኣጼ ምኒልክ ጊዜ የጠፉ ጥፋቶች ካሉ ለነዚያ ጥፋቶች የኣማራውን ህዝብ ሃላፊነት ውሰድና ይቅርታ በል የሚል ኣካል ቢነሳ ኣማራው ለራሱ ተበድያለሁ ባይ ነው። በፊውዳሉ ስርዓት በጭሰኝነት፣ በባርነት መከራየን ኣይቻለሁ:: በወቅቱ የተጠቀሙት ጥቂት ፊውዳሎች ናቸው:: ተውኝ እባካችሁ ይላል። በኣጼ ሃይለስላሴ ዘመንም ቢሆን የወሎ ርሃብ ሲመጣ ሃይለስላሴ ዓለም እንዳይሰማ ኣድርገው በዚያ ደረጃ ጨክነው ኣስጨርሰውኝ የለም ወይ? ደርግ ኣማራ ነው ካላችሁ ደግሞ የጎንደርንና የወሎን ወላድ እምባ ኣታዩም ወይ? ወዘተ. እያለ እያነባ ባለፉት ስርዓቶች የተጎዳውን ይቆጥራል። ኦሮሞው በበኩሉ በዚህኛውም ባለፈውም መንግስት ተነጥየ ተጎዳሁ፣ ባህሌ፣  ማንነቴ ተጎዳ ብሎ እያነባ ይናገራል፣ ትግሬው በበኩሉ ባለፈውም ሆነ ኣሁን የተመቸኝ ነገር የለም፣ የውስጥ ችግሬን እኔ ነኝ የማውቀው ተለይቼ ተበድያለሁ እያለ ያነባል፣ የደቡብ ህዝቡ ተበድያለሁ የኔን መከራ ማን ባየው እያለ እያነባ ይናገራል፣ ሱማሌው የኔ መከራ መቼ ነው የሚያቆመው? መከራየን እያየሁ ነው እያለ ያነባል። ጋምቤላው፣ ኣፋሩ ሁሉም በተናጠልም በቡድንም ተጎድቻለሁ እያለ ያነባል። ታዲያ እንዲህ በሆነባት ኣገር ብሄራዊ እርቅ ምን መልክ ይኖረዋል የሚለው ጥያቄ ላይ ነው መወያየት ያለብን።

በመጀመሪያ ግን እኛ ኢትዮጵያዊያን ያለፉ ታሪካዊ ችግሮች ኣጥንተን መፍትሄ ለመስጠት የታሪክ ተዓማኒነትም ችግር ኣለብን። በተለይ በኣሁነ ወቅት ፖለቲካው ከፋፍሎ የመግዛት ዘዴን የሚጠቀም በመሆኑ ኣንዳንድ በፈጠራ የሚጻፉ ታሪኮች ያለፈውን ታሪካችንን በሚገባ ኣይተን ብሄራዊ እርቅ ለማምጣት እንቅፋት ነው። የሆነ ሆኖ ግን በኢትዮጵያ ውስጥ ላለፈውም ሆነ ኣሁን ላለው ግፍና በደል ኣንድ ቡድን እንደ ቡድን ሃላፊነት ወስዶ ይቅርታ የሚልበት ሁኔታ የለም። በደቡብ ኣፍሪካም ሆነ በኣውስትራሊያ ወይም በሌሎች ኣገሮች እንደተፈጠረው ኣይነት ሃላፊነት ወስዶ የቡድኖችን እንባ የሚያብስ ጠፋ። በመሆኑም የኢትዮጵያ ምሁራን በዚህ ኣስቸጋሪ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ ብሄራዊ እርቅ ማለት ምን ማለት እንደሆነና ሁላችንን የሚፈውስ ኣሳብ በግድ ኣምጠው ሊወልዱ ይገባል።

በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ነባራዊ ሁኔታ የሚያሳየው ቡድኖች እንደቡድንም በጅምላም ባለፈው ጊዜ ለደረሰባቸው በደል ሁሉ ያለፈውንና ኣሁን ያለውን ስርዓት የታሪክ ተጠያቂ ማድረጉ ኣንዱ የስምምነቱ ኣሳብ ወለል ቢሆን መልካም ነው። ይሁን እንጂ ላለፉት ችግሮቻችን ቡድኖች እንደ ቡድን ተጎዳሁ የሚሉት ካለ ለዚያ ቡድን ጉዳት እውቅና መስጠት ኣንዱ የስምምነቱ ኣካል ሊሆን ይገባል። ኣንድ ቡድን ተጎዳሁ ተጎድቼ ነበር ሲል የለም ያንተ ጉዳት ትንሽ ነው የኔ ይበልጣል ማለቱ ብሄራዊ ፈውስን ኣያመጣም።ሰው ህመሙን የሚያውቀው ራሱ ነው። በመሆኑም ቡድኖች  የተጎዳነው ኣለ ሲሉ ማዳመጥና ሃዘንን መጋራት ለችግር እውቅና መስጠት ነው የኢትዮጵያ ብሄራዊ እርቅ መሰረቱ።  ኦሮሞው ኣጼ ምኒሊክ ጎድተውኛል ካለ ሌላው ብሄር ልክ ኣይደለም ኣልጎዱህም ማለቱ ለብሄራዊ እርቁ ኣይጠቅመንም። ኣንዱ ዜጋ ኣጼ ምኒሊክ  ካጠፉት ጥፋት ይልቅ የሰሩት ጀብዱ በተለይም ኢትዮጵያን ከውጭ ወራሪ ለመመከት ያደረጉት ተጋድሎ ከበለጠበት ቢወዳቸው ቢፎክርላቸው ሌላው ኢትዮጵያዊ መበሳጨትና ጥል ውስጥ መግባት የለበትም። ኣንድ መሪ ለኣንዱ ኢትዮጵያዊ ተወዶ ለሌላው የሚጠላ ቢሆንም ከዚህ ልዩነታችን ጋር ኣብረን መኖር እንችላለን። ኢትዮጵያዊ ለመሆን ሁሉ ሰው ኣጼ ምኒሊክን መውደድ ኣለበት ማለት ኣይደላም።ፕሬዚደንት ኦባማንና ፕሬዚደንት ቡሽን የሚወድም የሚጠላም በሰላም እንደሚኖረው እኛም ከልዩነት ጋር መኖርን መልመድ ያስፈልገናል።

ኣሁን እኛ ጋር ያለው የኮሙኒኬሽን ችግር ይመስላል። የኮሙኒኬሽን ችግሮች ምንጫቸው የእውነት መዛነፍ (distortion of truth) እንዲሁም የማንነት ፖለቲካ ውጤቶች ስለሆኑ ለነዚህ ችግሮች ራስን ሰለባ ኣለማድረግ ነው።በመሆኑም የኢትዮጵያ ብሄራዊ እርቅ ዋናው መሰረት እርስ በርስ መረዳዳት(understanding eachother) ነው ማለት ነው። ያለፈውን ህመማችንን በመደማመጥ ነው ልንፈታው የምንችለው። ችግራችንን ስንገልጥ የለም ያንተ ቁስል ትንሽ ነው የኔ ነው ትልቁና ኣንተ ስለ ብሶትህ ኣታንሳ ኣይባልም። ቢሆን ቢሆን ራስን ከውጭ ወደ ውስጥ ከውስጥ ወደ ውጭ የማየት ልብ ቢኖረን እሱ ነው ያለፈውንና ኣሁን ድረስ የቀጠለውን ችግራችንን የሚፈታው። በኣሁኑ ሰዓት እኔ ኦሮሞ መሆኔ ቀርቶ ትግራይ ሆኘ ብፈጠር ምን ይሰማኝ ነበር? ምን እሆን ነበር? ብሎ ቢያስብ በኣንጻሩ የትግራይ ህዝብ ኦሮሞው ኣማራው ተለይቼ ተጎዳሁ ሲል  በኣሁኑ ሰዓት እኔ ኦሮሞ ሆኘ ተፈጥሬ ቢሆን ምን ይሰማኝ ነበር? የሚል ከፍ ያለ መረዳት (understanding eachother’s pain and understanding each other’s feelings) በተለይ በሌሂቁ በኩል ቢታይ ነው የብሄራዊ እርቁ መሰረቱ የሚጠብቀው። ኣንድ ሰው ጉዳቴ ከፍተኛ ነው ሲል የለም ያንተ ትንሽ ነው የኔ ነው ትልቁ ጉዳት ወደ ማለት ማዘንበላችን የኮሙኒኬሽን ችግር ያመጣብናል። እውነቱን እንነጋግር ከተባለ እኛ ኢትዮጵያዊያን ያለፈውን ችግር  በብሄራዊ ይቅርታ ለመዝጋት የገጠመን ችግር ይሄው የኮሙኒኬሽን ችግር ነው። ያለመደማመጥና ህመምን ለመካፈል መድረክ ማጣት ትልቅ ችግሮች ሆነዋል። ሌላው ደግሞ ቅድም እንዳልኩት ያለፈውን ችግራችንን በብሄራዊ እርቅ ለመፍታት የነበሩትን በደሎች ወደ መድረክ ኣምጥቶ እውነትን ለመግለጥ ኣሁን ያለው መንግስት ታሪክን ስላቆራፈደውና ብርታትንም ሆነ ድካምን ከቡድን ማንነት ጋር እንድናያይዝ የሚገፋ ነገር በመኖሩ በከፍተኛ ሁኔታ እውነትን የማግኘትና የመዋጥ ችግር ይገጥመናል። በተጨማሪም  ኢትዮጵያዊያን ኣዳዲስ በሚወለዱ ታሪኮች ሳንደነብር ከስሜት በላይ ሆነን እርስ በርስ በመረዳዳትና ኣለ ለተባለው ችግር እውቅና በመስጠት ነገሩን ማርገብ ይጠበቅብናል።ከሁሉ በላይ ግን ኢትዮጵያ ያለፈውን ችግር ልታይበት የምትችልበት ኣንድ ሌላ ትልቅ ነገር የዛሬው ይዞታዋ ነው። በፊት የነበሩ ማህበራዊና ፓለቲካዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ኣሁን ድረስ እየተንከባለሉ መጥተው ስለሚገኙ ኣሁን ያለውን በቡድኖች መካከል ያለውን ክፍተት በሪስቶሬቲቭ ፍትህ ልትፈታው ይገባታል።  በትምህርት፣ በፖለቲካ ተሳትፎ በባህልና በቋንቋ ኣካባቢ ያለውን ችግር ኢትዩጵያ ለመፍታት ስምምነት ውስጥ መግባት ኣለባት። ይህ ስምምነት ነው ኣንዱ የብሄራዊ እርቁ ይዘት።  ሪስቶሬቲቭ  ፍትህ ስንል በማህበራዊ ተቋማት ግንባታ ይሁን ከፍ ሲል በገለጽናቸው ሁኔታዎች የተጎዱ ኣካባቢዎችን በኣፌርማቲቭ ኣክሽን ዘዴዎች ለመፍታት ስምምነት ላይ መጀመሪያ መድረስ ኣለብን። ይህ የብሄራዊ እርቁ ሰነድ የሚይዘው ኣንዱ ጉዳይ መሆን ኣለበት።

በመሆኑም ኢትዮጵያ በስምምነቱዋ ወቅት የምታካትታቸው ጉዳዩች በግልጽ መጀመሪያ መቀመጥ ኣለባቸው። ቡድኖች እንደ ቡድን ሁሉም ተበድለዋልና ብሄራዊ እርቁ  ሁሉንም ሊክስ የሚችልና ኮሙኒኬሽንን የሚያዳብር መሆን ኣለበት። በዓለማችን የሚነሱ ጦርነቶች ኣብዛኛዎቹ ማለት ይቻላል ምክንያታዊነት ያላቸው ኣይደሉም ኣብዛኛዎቹ ከኮሙኒኬሽን ችግር ጋር የተያያዙ ናቸው። ኣንዳንዴ ቡድኖች የተጣሉበትን ሁኔታ በውል ሳያውቁት ብዙ ይዋጉና ብዙ ሰው ካለቀ በሁዋላ ይታረቃሉ። የሚገርመው ሲታረቁና ስሜታቸው ሲረጋ የከፈሉት ዋጋ እንዲሁ ሜዳ ላይ ሆኖ የሚያገኙበት ጊዜ ይኖራል። በመሆኑም ብሄራዊ እርቁ በቡድኖች መካከል ያለን ኮሙኒኬሽን ለማስተካከል መላ ሊወልድ ይገባዋል።

ከፍ ሲል እንዳልነው ብሄራዊ እርቅ በኢትዮጵያ የሚኖረው መልክ ሁሉንም በመካስ ላይ ሁሉንም ችግሮች እውቅና በመስጠት ላይ የተመሰረተ መሆን ይኖርበታል። በተለይ ያለፈውን ችግራችንን ለመፍታት ችግሩ ከኮሙኒኬሽንና ከስሜት ሃያልነት ጋር የተያያዘ በመሆኑ በረጋና በሰከነ መንፈስ ዜጎች ያለፈውን ችጋራቸውን በጋራ እውቅና ሰጥተው ሲንከባለል ለመጣው ችግር ደግሞ ኣፈርማቲቭ ኣክሽንስና ሌሎች የርስበርስ የመካካሻ ዘዴ ተጠቅመው  ፈውስን ማውረድ ኣለባቸው። እንዲህ ስናደርግ ብሄራዊ እርቁ ሁለቱን ርምጃዎች የሚራመድ ሲሆን ሌላ ሶስተኛ ጉዳይ ደግሞ በውስጡ ሊያቅፍ ይገባዋል :: ይህ ሌላው የእርቁ ፓኬጅ የሚይዘው ደግሞ ኣዲሲቷን  ኢትዮጵያን እንደገና ለማነጽ እንዴት ኣብረን እንውጣ? እንዴት የጋራ ቤታችንን ኣብረን እናጥብቅ የሚለውን ያካትታል:: በመሰረቱ ይሄ ጉዳይ ቀላልም ከባድም ነው። ቀላል የሆነበት መንገድ በኣብዛኛው ፖለቲከኛና ሌሂቅ ዘንድ ቅንነቱ ካለ መፍትሄው ቀላል ስለሆነ ሲሆን ጠማምነቱ ካለ ደግሞ   ፈተና ነው።

በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ብሄራዊ እርቅን በኢትዮጵያ የሚያየው እንደዚህ ነው። በዚህ ጽንሰ ሃሳብ መሰረት ብሄራዊ እርቁ ሪስቶሬቲቭ ጀስቲስን መሰረት ያደረገና  በሚያድግ ዴሞክራሲ ችግሮችን ሊፈታ የሚችል ስምምነት ማለት ነው። ይህ ማለት ግን ሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ ቦታ የለውም ማለት ኣይደለም። በኣሁኑ ሰዓት በከፍተኛ ሙስናና ከፍተኛ ወንጀል እየፈጸሙ ያሉ ሰዎች ይህንን ኣሳባችንን እያዩ እንደ ጅልነት ኣይተው ከስልጣን እስኪወርዱ በግፋቸው እንዲቀጥሉ በር ኣይከፍትም።

የብሄራዊ እርቅ ሰነዱ እንደነዚህ ኣይነት ሰዎችን በቡድን እያየ ሳይሆን በግለሰብ ደረጃ ወደ ፍርድ ሊያመጣቸው መቻሉ ኣያጠያይቅም። እንደ ቡድን እንደ ሃገር ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻችንን ዝግ እያለ ሊሰራጭ በሚችል የሪዲስትሪቢዩሽን ዘዴ ተመጣጣኝ እድገት ለማምጣት መስማማት፣ ፖለቲካዊ ተሳትፎን ከባህላዊ ውህደት ስምምነት ኣንጻር ኣይቶ ከብሄር ፖለቲካ ኣውጥቶ በኣንድ ብሄራዊ ማንነት ስር ለመገንባት መስማማት፣ ዋና የሃገሪቱን ቋንቋዎችን ቁጥር  መጨመር ኣጠቃላይ ፈውስን ለማምጣት ይጠቅማል።

ኢትዮጵያ ሪስቶሬቲቭ ጀስቲስ ላይ እንድታተኩር የሚያደርጋት ለዘላቂ ሰላምና ልማት ኣንድነት የሚረዳት ሲሆን ይህ የፍትህ  ኣሰጣጥ ዘዴ በኢትዮጵያ ቡድኖች ዘንድ የተባረከና የሚበረታታ ነው። የኦሮሞ ስርዓትን ብናይ ለሪስቶሬቲቭ ጀስቲስ ትልቅ ቦታ ኣለው። ይቅር ማለትን፣ በዳዩን ከመቅጣት ይልቅ ተበዳዩን መካስን ያበረታታል። ኣማራው ኣካባቢ ያለውን የሽምግልና ስርዓት ስናይ በኣብዛኛው ሪስቶሬቲቭ ጀስቲስ የሚበረታታበት ሁኔታ ኣለ። በደቡብ፣ በምስራቅ በተለይም በሶማሌ ክልል ይህ የፍትህ ስርዓት ከፍተኛ ተጽእኖ ኣለው።

የሃይማኖት ዳራችንም ቢሆን ወደ መቶ ፐርሰንት የሚጠጋው ህዝብ ሃይማኖተኛ በሆነበት ኣገርም ይህ የፍትህ ስርዓት ሊሸከመው የሚችል በተፈጥሮው የተደራጀ ተቋም በመኖሩ ተመራጭ እንዲሆን ያደርገዋል።

ሌላው ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ባለፈው ጊዜ በግድ በሆነ ኣሲምሌሽን ጠፉ የሚባሉ ባህሎች ካሉ እነሱን የማስመለስ (Restoration and revival) ስራ ለመስራት መስማማቱ ነው ኣንዱ የእርቁ ሰንድ የሚይዘው ጉዳይ። የጠፉና በመጥፋት ላይ ያሉ ጠቃሚ ባህሎች ካሉና ቡድኖች የሚቆጩባቸው ከሆነ የማስመለስ ፖሊሲ ኣውጥቶ ቡድኖችን ሁሉ ተባብሮ ለመካስ ኪዳን መግባት። ቡድኖች ኣጣናቸው የሚሉዋቸውን በሙሉ ለማስመለስ ባይቻልም ኣብዛኛውን በመመለስ የቡድኖችን ልብ ማሳረፍ ይቻላል።

ሌላው የብሄራዊ እርቁ ሰነድ ሊይዘው የሚገባው ጉዳይ ለወደፊቱዋ ኢትዮጵያ የሚሆን ኣስተዳደራዊ ባህልን የመገንባት ስምምነት ሲሆን ይህም ዴሞክራሲ ነው። ቡድኖች በመጀመሪያ ዴሞክራሲ ከኣሁን በሁዋላ ያስተዳድረን  መንግስታት ቢቀያየሩም ዴሞክራሲ ግን የጋራ ባህላችን ይሁን የሚል ስምምነት ውስጥ ሊገቡ ይገባል። ይህ ኣስተዳደራዊ ባህል የጋራ የሁላቸው በመሆኑ ወደፊት ለህይወታቸው መሪ ይሆናል ማለት ነው።

ሌላው መሰመር ያለበትና የስምምነቱ ኣንዱ ኣካል ሊሆን የሚገባው ለመልካም ታሪኮቻችንም እውቅና መስጠት ነው። ኢትዮጵያን የመከራ ቤት ብቻ ኣድርጎ ከማየት የኣፍሪካ መቀመጫ ያደረጋትን የነጻነት ታጋይነቱዋን ማስታወስና ለነዚህ ታሪኮቻችን ደግሞ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ኣስተዋጾ በማድረጋቸው እውቅና ሊሰጡት ይገባል። ይህ ኣይነቱ ስሜት ሚዛናዊ የሆነ ስሜትን ከመፍጠሩም በላይ ኣገር ኣለን ስንል የምንመካባቸው ብዙ ኣኩሪ ታሪኮች እንዳሉንም ስለሚያደርግ ነው።

በሌላ በኩል ደግሞ የስምምነታቸን ሰነድ ኣንዱ ሊይዘው የሚገባው ነገር የማትከፋፈል ኢትዮጵያን ለትውልድ ማሳለፍ ነው። መንግስት መጥቶ መንግስት ሲሄድ ቋሚ ዶግማ የሆነ ስምምነት ሆኖ ሊቀመጥ የሚገባው ጉዳይ ነው። የወደፊቷን ኢትዮጵያን እንደገና ማነጽ ማለት ይሄው ነው።

 

ማጠቃለያ

በቅርቡ ከኔልሰን ማንዴላ ሞት ጋር በተያያዘ ዓለም ያሳየችውን ስሜት ስናይ ያስደንቃል።በኔልሰን ማንዴላ ሞት ምክንያት የዛሬይቱ ዓለማችን በሚያስደንቅ መልኩ መነቃነቋ፣ ያ ሁሉ መሪ ወደ ደቡብ ኣፍሪካ መጉረፉ የሚያሳየው የሃያ ኣንደኛዋ ክፍለ ዘመን ዓለም ለብሄራዊ እርቅና ይቅርታ የሰጠችውን ታላቅ ክብርና ቦታ ነው።ኢትዮጵያዊያንም ከዚህ የምንማረው ኣለ:: ኢትዮጵያ ብህዙ በመሆኑዋ ይህ ተፈጥሮዋ በስምምነት ላይ የተመሰረተች  ኣገር እንድትሆን ያስገድዳታል:: በመሆኑም በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ያስፈልገናል የምንለው ኣንዱ መነሻ ይሄ ነው። እንዴት ወደ ስምምነት እንገባለን? በምን መንገድ ነው ወደዚያ መስመር የምንገባው? ተግባራዊ ሂደቱ ምንድነው? ካልን ኣንዱ መንገድ ብሄራዊ እርቅ ማምጣት ነው። ከፍ ሲል እንዳልነው ብሄራዊ እርቅ ማለት በኢትዮጵያ ኣንዱ በዳይ ሌላው ካሳ የሚሰጥ ሳይሆን ርስበርስ የሚረዳዱበትና ሁሉም የሚካሱበት የእርቅ ኣሳብ ነው። በዋናነት ብሄራዊ እርቁ ያለፈውን ችግር መፍታት ኣሁን የዘለቀውን ችግር ማቆም ሆኖ ከሁሉ በላይ ግን ኢትዮጵያን እንደገና ለማነጽ የስምምነት ነጥቦችን ኣውጥቶ በነዚያ ስምምነቶች ዙሪያ መስማማት ነው። እነዚህ የስምምነት ኣጀንዳዎች የሃገሪቱ ዶግማዎች ይሆኑና ዘላለማዊ ኪዳን ይሆናሉ። ይህ ኪዳን ከህገ መንግስቷም በላይ ሆኖ የሚኖር ይሆናል።። ህገ መንግስት የሚያረቁ መንግስታትም ከነዚህ ዶግማዎች ኣንጻር ህጎችን ሊያወጡ ይገባል። ይህ የእርቅ ሰነድ በሃይማኖት መሪዎች፣ በባህል መሪዎች በፖለቲካ ፓርቲዎችና በሲቪክ ማህበራት ዘንድ ሁሉ የሚቀመጥ የሚከበር ትልቅ ኪዳን መሆን ኣለበት።ኢትዮጵያ በእንደዚህ ኣይነት ለየት ባለ ቅርጽ ብትተዳደርስ? ከህገ-መንግስቷም በላይ ሌላ ዶግማ የሆነ ኣዲስ ኪዳን ቢኖራት ጥሩ ኣይሆንም ?

መቼም ይሄ ተግባር የናፈቀው ህሊናችን ጥያቄ ማንሳቱ ኣይቀርም። ይህ ብሄራዊ እርቅ የሚባለው ነገር መቼ ነው መካሄድ ያለበት? ተዋንያኑስ እነማን ይሆናሉ? የሚል ተግባራዊ ጉዳዮች ይመጣሉ። በኢትዮጵያ ብሄራዊ እርቅ ማለት የተጣሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች መታረቅ፣ ወይም ውህደት ማድረግ ማለት ኣይደለም። በርግጥ የነዚህ ፓርቲዎች ውህደትና ስምምነት ለብሄራዊ እርቁ ከፍተኛ ኣስተዋጾ ኣለው። ኣሁን የምናወራውን ሰፊ ኪዳን ለመፈጸም ነው። ዓለምን የሚያስደምም ስምምነት ተስማምተን ኢትዮጵያን እንደገና ልናቆም ነው። ተዋንያን የሚሆኑት የተለያዩ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት ቡድኖች፣ ሲቪክ ማህበራት፣ ባህላዊ ቡድኖች ዜጎች ሁሉ ናቸው። ከኣለማቀፉ ማህበረሰብም ታዛቢ ኣስገብታ ይህንን ስምምነቱዋን ለኣለም ማሳየት ኣለባት። ከዚያ በሁዋላ ኢትዮጵያ ታላቅ ድግስ ደግሳ ያን የተስማማችበትን ቀን ዘወትር የምታከብረው የኢትዮጵያ ዳግም ምስረታ (Foundation day) ቀን ብላ ያን ቀን ዘወትር በየዓመቱ ታከብረዋለች።ይሄ መሆን የሚችል ነው።

ኢትዮጵያ ይህን የእርቅ ኪዳን የምትገባው ኣሁን ያለው መንግስት ወደ እርቅ ከመጣ ብቻ ኣይደለም። ይህ መንግስት ለዚህ እርቅ ሁኔታዎችን ቢያመቻችና ኣብሮ ቢሳተፍ ታሪክ ያመሰግነዋል። ነገር ግን በነውጥም ሆነ በጠመንጃ ይህ መንግስት ከወደቀ በሁዋላም ኢትዮጵያ የግድ ወደዚህ ኪዳን ውስጥ መግባት ስላለባት ከወዲሁ መዘጋጀት ያስፈልጋል። ባለፈው ታሪካችን የጠፋው ይሄ ነው። ለውጦች ሲመጡ ብሄራዊ እርቅ ሳይደረግ ኣሸናፊው ተሽናፊውን እየረገመ የተሻልኩ ነኝ እያለ ስለመጣን ብሄራዊ ችግሮቻችን እየባሱ መጥተዋል። ኣሁን ግን በየትኛውም ሁኔታ ቢሆን ኢትዮጵያ በዚህ የእርቅ ኣሳብ ውስጥ ማለፍ ኣለባት። ይሄ የግድ ነው።የብሄራዊ እርቁን የሚመራውና የእርቅ ኣሳቦችን የሚያመጣውን ኮሚሽን ኣገር ወዳድ የሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪክ ማህበራት ሚዲያዎችና ኮሚኒቲዎች ከፊታቸው ያለውን የልዩነት ተራራ በጎን በኩል ዞረው ኣልፈው ይህን ሰነድ የሚያዘጋጁና መላ የሚፈጥሩ ኣካላትን ሊፈጥሩ ይገባል።ይሄ ሰው የሚሰራው ኢትዮጵያዊያን ልንሸከመው የምችለው ሃላፊነት ነው። ኣሁን ባለው የፖለቲካ ኣሰላለፍ ኢትዮጵያ የጎደላት ይሄ ነው። ኣልፎ ኣልፎ የተለያዩ ፓርቲዎችን ኣገናኝቶ በማነጋገር የእርቅ ኣሳብን ለማዳበር የሚሰራ የለም ማለት ይቻላል። ከዚህም በተጨማሪ በየጊዜው የሚመጡ ለችግራችን የሚሆኑ የመፍትሄ  ኣሳቦችን የሚያጠናና የሚያደራጅ ባለመኖሩ ወርቅ የሆኑ ኣሳቦች ሁሉ ባከኑ። ለዚህም ኣንድ ጠርናፊ እውነትን የሚያፈላልግ የእርቅ ኣሳቦችን የሚያዳብር ተቋም ያስፈልገናልና በዚህ ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትኩረት ሰጥቶ መላ ሊለው መስሎኝ ነው።

እግዚኣብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!

ቸር እንሰንብት

geletawzeleke@gmail.com

ወደ ሃገር ለመሄድ እጃቸውን የሰጡ ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ ዛሬም የብሶት ድምጻቸውን ያሰማሉ (የድምጽ ዘገባ)

$
0
0

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)


ነቢዩ ሲራክ
ሁለተኛ ወር የያዘውን የሪያድ መንፉሃን ሁከት የኢትዮጵያውያንን መሞትና መቁሰል ብሎም መፈናቀል ተከትሎ የሳውዲ ሪያድ የኢንባሲና የጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት በባህር በሃጅና ኦምራ የመጡትን ጨምሮ ከአሰሪዎቻቸው ጋር የማይሰሩ ዜጎች በሳውዲ ህግ መሰረት ህገ ወጥ ናቸውና ወደ ሃገራቸው እንዲገቡ ተደጋጋሚ ማስታወቂያና ምክር ማስተላለፉ ይታወሳል። ይህንን ማስታወቂያ ተከትሎ ከ150 ሽህ በላይ ዜጎች ወደ ሃገር የገቡ ሲሆን ወደ ሃገር ለመግባት አቅማምተው የነበሩት ፍተሻው ጥንከር እያለ ሲመጣ ወደ ሃገር ለመግባት እጃቸውን በመስጠት ላይ ናቸው። ወደ ሃገር እንግባ ብለው በተደረገው ጥሪ እጃቸውን የሰጡት መኖሪያና የስራ ፈቃድ የነበራቸው ዜጎች ግን እዚህ በጅዳ ሽሜሲና በሪያድ እስር ቤቶች በደልና እንግልት እየደረሰብን ነው ሲሉ ምሬታቸውን ገልጸውልኛል።
በደል ብሶታቸውን አዘገጃጅቸዋለሁ ፣ በዛሬ የጀርመን ራዲዮ ዜና መጽሔት ይከታተሉ። ( የዜና መጽሔቱ 13ኛ ደቂቃ ላይ ይገኛል)
ሰላም

የመቀለ ወጣቶች ከህወሓት መሪዎች ጋር ተጋጩ

$
0
0
የመቀሌ ከተማ (ፎቶ ፋይል)

የመቀሌ ከተማ (ፎቶ ፋይል)

አብርሃ ደስታ በፌስቡክ ገጹ እንደዘገበው፦

ዛሬ ሐሙስ ታህሳስ 24, 2006 ዓም በኮብልስቶን ስራ የተሰማሩ (ና ለመሰማራት በማህበራት የተደራጁ) የመቀለ ወጣቶች በመቀለ ከተማ ማዘጋጃቤት አዳራሽ ተሰብስበው ነበር። የተሰበሰቡበት ምክንያት በጨረታ የተወዳደሩበት የኮብልስቶን ግንባታ መሰረዙ ሊነገራቸው ተብሎ ነበር።

ባለፈው ዓመት በኮብልስቶን ስራ የተሰማሩ ወጣቶች አብዛኞቹ መክሰራቸው ይታወሳል። የከሰሩበት ምክንያት ደግሞ ለኮብልስቶን ስራ ተብሎ ከዓለም ባንክ የተከኘ ገንዘብ በሐላፊዎች አለ አግባብ መመዝበሩ ነበር። የኮብልስቶን ገንዘብ የሰረቁ ባለስልጣናት መታሰራቸው ይታወሳል።

አሁን በወጣው ጨረታ መሰረት ግን ለስርቅ የሚሆን የሚተርፍ የኮብልስቶን ገንዘብ አይኖርም። በዚህ ምክንያት የህወሓት መሪዎች ጨረታው ለመሰረዝና ሌላ አዲስ ጨረታ ለመክፈት ወስነዋል። ወጣቶቹም የህወሓት መሪዎች የወሰዱት እርምጃ ክፉኛ ተቃውሞውታል። ወጣቶቹ ለጠየቁት ጥያቄ ተገቢ መልስ ባለመግኘታቸው ስብሰባው ረግጠው ወጥተዋል። የአደራሹ በር በመዝጋት ስብሰባው ረግጠው እንዳይወጡ ጥረት የተደረገ ቢሆንም አልተሳካም።

ወጣቶቹ ነገ ጠዋት (ዓርብ) ወደ ክልል ቢሮ ተሰባስበው ይሄዳሉ። የክልል መንግስት መፍትሔ ካልሰጣቸው የተቃውሞ ሰልፍ እስከማድረግ ይደርሳሉ።

ይህ የኮብልስቶን ጉዳይ ባብዛኞቹ የትግራይ ክልል ከተሞች ትልቅ አጀንዳ ሁኗል።

(ኮብልስቶንም … ንትርክ በዛባት)

ያለፉት ስህተቶች ትምህርት እንጂ ማነቆ አይሁኑ –ግርማ ካሳ

$
0
0

ግርማ ካሳ  

እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር፣  ኖቬምበር 17 ቀን 1996 ነበር። በሰርቢያ (የቀድሞ ዩጎስላቪያ) ፣  የክልል ምርጫ ይደረጋል።  በቩክ ድራስኮቪች የሚመራዉ SPO ፣ በቬስና ፔሲች የሚመራዉ GSS እና ሌሎች ድርጅቶች በአንድ ላይ ሆነው አብላጫ ድምጽ ያገኛሉ። ነገር ግን  በወቅቱ የነበሩ አምባገነን ባለስልጣናት፣ እነ ስሎቦዳን ሚሎሶቪች አጭበረበሩ።  ከኖቬምበር 17 1996 እስከ ፌቡሩያሪ 11 1997 ድረስ፣ «ያጄድኖ» የሚል፣  ሕዝባዊ ተቃዉሞዎች በስፋት ተደረጉ። ባለስልጣናቱ፣  የሕዝቡ ሰላማዊ ተቃዉሞ አይሎ መምጣቱን ሲያዩ አፈገፈጉ። የተቃዋሚዎች ስብስብ በክልል ምርጫዉ ያገኙትን ምርጫ፣ ተቀበሉ። ሊበራል ዴሞክራቱ ዞራን ጂንጂች የአገሪቷ መዲና የቤል ግሬድ ከንቲባ ሆኑ።

 

ብዙም አልቆየም፣ በተቃዋሚዎች መካከል ችግር መታየት ጀመረ። በቩክ ድራስኮቪች የሚመራዉ ፓርቲና  በዞራን ጂንጂች በሚመራዉ ፓርቲ መካከል ልዩነቶች ተፈጠሩ። መካረር መጣ። የሕዝብን ጥያቄ አንግቦ በጋራ መቆም ተሳናቸው። በአደባባይ መወጋገዝ ጀመሩ። በአመቱ አገራዊ የፕሬዘዳንት ምርጫ ሲደረግ የሚሎሶቪች የሶሻሊስት ፓርቲ በቀላሉ ስልጣኑን ጨበጠ። የተለፋበት፣ የተደከመበት ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ከሸፈ። አምባገነኖች አሸነፉ። በሕዝብ ትግል የተገኙ ዉጤት እንደገና ተቀለበሱ። ዞራን ጂንጂችም ከናካቴዉ ከተመረጡበት የቤልግሬድ ከንቲባነት ተነሱ።

 

በ1998 በየክልሉ ተማሪዎች «ኦትፖር» ( በሰርቢያን ቋንቋ እምቢተኝነት) በሚል ስም ከታች ወደ ላይ የሆነ እንቅስቃሴ ጀመሩ። የተከፋፈሉ የፖለቲካ ደርጅቶች በአንድ ላይ እንደገና ተሰባሰቡ። ካለፉት ስህተቶች በመማር፣ ፍጹም ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ ለሚቀጥለው ምርጫ መዘጋጀት ጀመሩ። ከፍተኛ ጫና እየተደረገም ዝግጅቱ ተጧጧፈ። የገዥዉ ፓርቲ ደጋፊዎችን የመሳብ ሥራ በስፋት ተሰራ። በዚህም ምክንያት በርካታ የገዢዉ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ተቃዋሚዎችን መቀላቀል ጀመሩ። ኢቫን ስታምቦሊች ፣ የሚሎሶቪች አጋር የነበሩ ፖለቲከኛ ፣ ተቃዋሚዎች በመቀላቀላቸውም በሚሎሶቪሽ የደህንነት ሰራተኞች ታፍነው ተገደሉ።

 

ሴፕቴምበር 2000 ዓ.ም ምርጫ ተደረገ። የሚሎሶቪች ምርጫ ቦርድ፣ አሁንም የተጭበረበረ የምርጫ ዉጤት ይፋ አደረገ።  ያንን አስከትሎ  ኦክቶቦር  2000 ዓ.ም ፣ ትልቅ ተቃውሞ ሰልፍ ተደረገ። ምርጫ ቦርድ የምርጫዉን ዉጤት ወደ ነበረበት እንዲመልስ ተገደደ። የተቃዋሚዎች እጩ የሆኑት  ኮስቶኒሳ እንዳሸነፉ ተገለጸ። የሚሎሶቪች ስልጣን ፍጻሜ ሆነ። የሰርቢያ ሕዝብ የማይቀለበስ ድል ተቀዳጀ።

 

ይሄንን ያለ ምክንያት አይደለም ያመጣሁት። በሰርቢያ፣ በመጀመሪያዉ ምርጫ  የተከሰተው፣ በኢትዮጵያም በምርጫ ዘጠና ሰባት ከተከሰተው ብዙ የሚለይ አይደለም። ያኔ በቅንጅት ጊዜ የሕዝብ ጉልበት አያሎ የወጣበት ወቅት ነበር። ነገር ግን በተቃዋሚዎች መካከል በተፈጠሩ ልዩነቶች፣ በቀላሉ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ስልጣን ላይ ለመቆየት ቻለ። (በገዢው ፓርቲ የደረሰው ወከባ፣ ግድያ፣ እሥር፣ እንግልትን ጫና ቢኖርም፣ በዋናነት የተቃዋሚዎች ችግር ነው አገዛዙን ያቆየው ብዬ ነዉ የማምነው)

 

ሰርቦች ጠመንጃ አላነሱም። ሰርቦች ለዉጥ ማምጣት አይቻልም ብለው አላወጁም። ሰርቦች ተስፋ አልቆረጡም። እኛ ኢትዮጵያዉያን ግን ተስፋ ቆረጥን። ፎጣችንን መሬት ላይ ጥለን፣ አምባገነንነትን አሜን ብሎ የመቀበል አዝማሚያ አሳየን። «ተቃዋሚዎች አይረቡም። ያኔ ደግፈናቸው ጉድ አላደረጉንም እንዴ ? አርፎ መቀመጥ ይሻላል፣ ሰላማዊ ትግል አይሰራም ….» የሚሉ ጨለምተኛና የሽንፈት አባባሎችን ማሰማት ጀመርን።

 

የገዢዉ ፓርቲ ሰዎችም፣ ስልጣን ላይ ለመቆት የሚያስችላቸው፣  ይሄዉ የተቃዋሚዎች መከፋፈልና የሕዝቡም ተስፋ መቁረጥ ስለነበረ፣  በሚቆጣጠሯቸው ሜዲያዎች፣ ሕዝቡ በተቃዋሚዎች ላይ የበለጠ ተስፋ እንዲቆርጥ፣ ከፍተኛና ሲስቴማቲክ፣  ተቃዋሚዎች የማጥላላትን የማሳነስ ዘመቻቸዉን አፋፋሙ። ጠንካራ የሚሏቸውን የተቃዋሚ መሪዎችና ጋዜጠኞች ያለ ርህራሄ አሰሩ። ብርቱካን ሚደቅሳን አሰቃይተውና ሰባብረው (ለስድስት ወራት ሁለት ሜትር በሁለት ሜትር ጨለማ ቤት ዉስጥ እንዳስቀመጧት) ለስደት ዳረጓት። «እነርሱን ያየህ ተቀጣ» በሚል፣  በአንዱዋለም አራጌ፣ በእስክንደር ነጋ፣ በርዪት አለሙ፣ በዉብሸት ታዬ፣ በበቀለ ገርባ እንዲሁም በሌሎች ..ሰላማዊ ወገኖቻችን ላይ፣ በተራ የዉሸት ሽብር ክስ፣  ኢፍትሃዊነትና ኢሰብአዊነት የተሞላበት ግፍ መፈጸማቸዉን ቀጠሉ። በሕዝቡ  አይምሮ ዉስጥ፣ እነርሱን ማንም ሊነካቸው የማይችሉ፣  ግዙፎች (ኢንቪሲብል) እንደሆኑ ለመሳል መሞከርና፣ ሕዝቡ እርስ በርስ ተፈራርቶ እንዳይደራጅ፣ እንዳይነጋገር፣ እንዳይተማመን፣ በዘር፣ በኃይማኖት በጥቅም እንዲከፋፈል፣  ማድረጉን ተያያዙት።

 

ነገር ግን ኢትዮጵያዉያን መንቃት ያለብን ይመስለኛል። ከሰርቦች መማር ያለብን ይመስለኛል። አምባገነኖች ኃይለኛ የሆኑ ይመስላሉ እንጂ ሁልጊዜ ባዶ መሆናቸዉን መረዳት አለብን። ሕወሃት/ኢሕአዴግ የሕዝብ ድጋፍ የሌለው፣ በሙስና የተዘፈቀ፣ ለሕዝብና ለዜጎች ከበሬታ የማያሳይ፣ ዜጎችን ሽብርተኞች እያለ የሚያሸብር፣ የበሰበሰ ድርጅት እንደሆነ በግልጽ እየታየ ነዉ።

 

እንግዲህ «ትላንት ወድቀናል ብለን፣ የትናንቱ ጠባሳችንን እያየን ወደፊት ከመራመድ መቆጠብ የለብንም» እላለሁ። ከስህተቶቻችን ተምረን፣ ያለፈው ታሪካችን በአይምሯችን እየፈጠረ ካለው ጎታች ጫና ተላቀን፣ ይሄንን ዘረኛና አምባገነን ስርዓት ለመቀየር በቁርጠኝነት መነሳት የግድ ነዉ። ቁልፉ በእጃችን ነዉ። በርግጥ ለዉጥ ማምጣት እንችላለን። ጥያቄው «ፍላጎቱ አለን ወይ?» የሚል ነዉ።

 

እያንዳንዳች ወደ ራሳችን እንመልከት። እራሳችንን እንጠይቅ። «እስከመቼ ነዉ፣  በአገራችን እንደ ባይተዋር ፈርተን እና አንገታችንን ደፍተን የምንቀመጠው ?» ማለት እንጀመር። በየወረዳችን፣ በየአካባቢያችን፣  ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ድርጅቶችን እንቀላቀል። የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ፣ ጠንካራና አገር ሰፊ የኢትዮጵያዊትነትና የሰለጠነ ፖለቲካ የሚያራምድ ድርጅት ነዉ። በመቀሌ፣ አርባ ምንጭ፣ ጂንካ፣ አዳማ ፣ አሶሶ …በአገርቷ ክፍሎች ሁሉ ብትሄዱ አንድነት በዚያ አለ። አንድነትን እንቀላቀል። አንድነትን እንደግፍ። የሰማያዊ ፓርቲ ፣ መኢአድ፣ ኤዴፓ፣ አረና ..ሁሉም በፊናቸው የሕዝብን ጥያቄ እያሰተጋቡ ነው። እንቀላቀላቸው። እንደግፋቸው። ልዩነቶቻቸውንም አጣበው ፣ የበለጠ ኃይልና ጉልበት ኖሯቸው ሰላማዊ፣ የኢትዮጵያዊነት የሰለጠነን የፖለቲካ ትግል ይመሩ  ዘንድ፣ እንዲሰባሰቡ፣ እንዲዋሃዱ እናበረታታቸው።

 

ፈረንጆች ኒው ዪር ሬዞሉሽን (የአዲስ አመት ዉሳኔ) ይሉታል። እንግዲህ፣ በዚህ የ2014 አዲስ አመት፣ የሁላችንም ምኞት፣ ጥረትና ዉሳኔ፣  በአገራችን መልካም ለዉጥ እንዲመጣ፣ የድርሻችንን በሃሳብ፣ በገንዘብ፣ በጸሎት ለማገዝ ይሁን። የሌሎች ሕመምና ስቃይ ይሰማን። ዝምታን በቃ እንበል። እግዚአብሄር አምላክም ረድኤቱን ያብዛልን!

 

comment pic

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ልዩ ጉባኤው የአቋም መግለጫ

$
0
0

UDJዛሬ በደረስንበት 21ኛው ክፍለዘመን በአለማችን የሚገኘው ሕዝብ ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቹ በተከበሩበት ሁኔታ መመራት ይሻል፡፡ በዚህ ዘመን አምባገነን መሪዎችና መንግስታት በየትኛውም መስፈርት ስልጣን ላይ የመቆየት እድል የላቸውም፡፡ በዚህ ረገድ በቅርብ አመታት ውስጥ የማይደፈሩና እንደ ፈርኦን ይመለኩ የነበሩ አምባገነን መንግስታት በህዝባዊ ማዕበል ተጥለቅልቀውና ተንጠው መቀመቅ ሲወርዱ የአለም ህዝብ ሁሉ አስተውሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት የዲሞክራሲና የነፃነት ጥየቄ ከዳቦ ጥያቄ ይበልጥ አንገብጋቢ እየሆነ መጥቷል፡፡

የአለማችን አንድ አካል የሆነችው አገራችን ኢትዮጵያ የዘመናት የስልጣኔ ጉዞዋ የምድራችን ቁንጮ የታሪክ ባለቤት ያደርጋታል፡፡ በየዘመናቱ የተነሱ ገዢዎቻችን ሲጭኑብን የቆዩት የአገዛዝ ቀንበር ወገባችንን ቢያጎብጠውም የኢትዮጵያ አንድነትና ሉኣላዊነት ፍፁም ሳይሸራረፍ ተጠብቆ ዘመን እንዲሻገርና ለትውልድ እንዲተላለፍ የማይሻ ኢትዮጵያዊ የለም፡፡

ወታደራዊው ደርግ ከሥልጣን በተወገደ ማግስት ዲሞክራሲና ነፃነት የሰፈነበት የዜጎች ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች የሚከበሩባትን ኢትዮጵያ ለማየት ያልጓጓ ኢትዮጵያዊ አልነበረም፡፡ ህልማችን በእውነት ሳይፈታ ቀረ፣ ተስፋ ያደረግነው ነገር ከዓመት ዓመት እየጨለመ መጣ፡፡ ኢህአዴግ ባለፉት 23 ዓመታት የምኒሊክን ቤተመንግስት ቢቆጣጠርም የአገርን ህልውና ከመጠበቅና የህዝብ እንባን ከማበስ ይልቅ ዜጎችን መውጪያ መግቢያእያሳጣና የመከራን ገፈት እያስጨለጠ ጉዞውን ቀጥሏል፡፡ ስደቱ፣ እንግልቱ፣ ግርፋቱ፣ እስራቱ፣ ግድያው፣ አፈናው፣ ስቃዩ ከመቀነስ ይልቅ በየጊዜው እየከፋ ይገኛል፡፡

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ይህን ቀንበር ለመስበር እንደ መርፌ ቀዳዳ በጠበበው የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ እየተንቀሳቀሰ በመላው አገሪቱ ህዝብን ለትግል እያሰለፈ ይገኛል፡፡
ይህን እልህ አስጨራሽ ትግል ለመምራት ትልቁ የስልጣን አካል የሆነው ይህ ጠቅላላ ጉባኤ ታህሳስ 19 እና 20 / 2006 ዓ.ም ለሁለት ተከታታይ ቀናት ባደረገው ከፍተኛ ስብሰባ አያሌ አገራዊ ጉዳዮችን በማንሳት ተወያይቷል፡፡ የፓርቲውን ምክር ቤት ፣ የሥራ አስፈፃሚና የኦዲት ኮሚሽንን ሪፖርት በማድመጥ ጠንካራ ውይይት አካሂዷል፡፡

በመጨረሻም የአገልግሎት ዘመናቸውን ባጠናቀቁት የፓርቲው ፕሬዚደንት የተከበሩ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ምትክ የተከበሩ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራውን ፍፁም ግልፅና ዲሞክራሲያዊ በሆነ ምርጫ ተክቷል፡፡ የፓርቲውን ብሔራዊ ምክር ቤት እና የኦዲት ኮሚሽን አባላትንም በመምረጥ ጉባኤው ተጠናቋል፡፡

አባላቱ በጉባኤው ማጠናቀቂያ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ የሚከተለውን የአቋም መግለጫና ውሳኔ በማሳለፍ ተጠናቋል፡፡

1ኛ. ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ በአገሪቱ የሚደረገውን የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ ለማኮላሸት ነጋ ጠባ የሚያጠነጠነው እኩይ ሴራ የህዝቡን ስሜት ወደ ሌላ አቅጣጫ እና ጥግ እየገፋው ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ ፓርቲያችን አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በጀመረው የሰላማዊ ትግል ጉዞ የኢትዮጵያን ህዝብ የስልጣን ባለመብት ለማድረግ እስከመጨረሻው እንጥፍጣፊ በጥብቅ መታገል እንደሚኖርበት ይታመናል፡፡ በመሆኑም እኛ ከመላው አገሪቱ በዚህ ጉባኤ ላይ የታደምን የፓርቲ አባላትና አመራሮች ከመቼውም ጊዜ በላቀ መልኩ ለሰላማዊ ትግሉ ቁርጠኛ መሆናችንን እናረጋግጣለን፡፡
2ኛ. አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት የፓርቲያችንን እንቅስቃሴዎች እግር በእግር እየተከታተለና በሀሰት ውንጀላ በማጠልሸት በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዳናገኝ ጠቅልሎ በያዘው የቴሌቪዥን ጣቢያ ሰፊ የሆነ አፍራሽ ተልዕኮን እያስተጋባ ይገኛል፡፡ይህ ጉዳይ ህገ መንግስቱ ለመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ያመቻቸውን መንገድ ሙሉ ለሙሉ የሚጠቅም ነው፡፡ ከዚህ አንፃር አገር እየመራሁኝ ነው የሚለው ኢህአዴግ ፓርቲያችንን ከሽብር ድርጊት ከአሸባሪዎች ጋር ለማቆራኘት የሚያደርገውን እኩይ ሴራ አጥብቀን እናወግዛለን፡፡

3ኛ. በዚህ ልዩ ጉባኤ ወቅት በአካል በመቅረብ በገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ካድሬዎችና ታጣቂዎች በሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ አርቡር ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው የ 8 ዓመቷ ህፃን ስለእናት ማስረሻ ጥላሁን የደረሰባትን እጅግ ዘግናኝና ሰቅጣጭ የአካል ጉዳትአሳይታለች፣ ሁኔታው የጉባኤውን አባላት ክፉኛ ያስቆጣ ሆኗል፡፡ አባቷን እና የቤት እንስሳትን በጥይት ገድለው ህፃን ስለእናትን በጥይት አረር እጇን የቆረጡ እኝህ እኩያን ወንጀለኞች በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን፡፡
4ኛ. የገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ የአመራር ዘመን አገራችን ኢትዮጵያ በታሪኳ እጅግ የተዋረደችበትና ሉኣላዊነቷ የተደፈረበት ወቅት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ዜጎች የከፋ የሰብአዊ መብት ጥሰት ይደርስባቸዋል፣ይታሰራሉ፣ ይደበደባሉ፣ ይገደላሉ፣ ይሰደዳሉ ወዘተርፈ፡፡
ለስደት በተዳረጉባቸው አገራትም ዜጎቻችን በግፍ ሲገደሉና ሲደበደቡ እያን ነው፡፡ በቅርቡ በሳውዲ አረቢያና ሰሞኑን ደግሞ በደቡብ ሱዳን ኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ሞትና ስቃይ የእያንዳንዳችንን ልብ የሰበረ ጉዳይ ነው፡፡ ለዚህም ተጠያቂው ኢህአዴግ ነው፡፡
በመሆኑም ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ በመላው ዓለም እንደ ወንዝ ዳር አሸዋ ተበትነው ለሚንገላቱ ዜጎች ጉዳይ በአፅንኦት እየተከታተለ እንዲታደግና የመንግስትነት ግዴታውን ባግባቡ እንዲወጣ አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡
5ኛ. በአሁኑ ወቅት የገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ጥቂት ሹማምንት እጆቻቸውን እያስረዘሙ የአገርን ሀብት እየዘረፉ ናቸው፣ ሥርዓቱ ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ በሙስና የተጨማለቀ መሆኑን እየተጋለጠ ነው፡፡ ዜጎች ዛሬ የዕለት ጉርሳቸውን አጥተው ሲራቡና ሲጠሙ፣ወጣቶች የሥራ ዕድል ተነፍጓቸው በአሳፋሪ ሁኔታ ከአገር ሲሰደዱ፣ የኑሮ ውድነቱ ትውልዱን ግራ እያጋባ ነው፣ ህዝቡ ፍትህና መልካም አስተዳደር በማጣት ነጋ ጠባ የዜግነቱ ጉዳይ ጥያቄ በፈጠረበት ሁኔታ የነገዋን ኃያልና የበለፀገች ኢትዮጵያን አይደለም ማየት ይቅርና የህልውናዋ ጉዳይም አጣብቂኝ ውስጥ የገባበት ሰዓት ላይ ደርሰናል፡፡ በአገሪቱም አስከፊ ብሔራዊ ቀውስ ይፈጠራል ብለን እንሰጋለን፡፡
ከዚህ አንፃር ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ብሔራዊ መግባባትን የሚያሰፍን መድረክ እንዲያዘጋጅ አበክረን እንጠይቃለን፡፡
6ኛ. ኢቴቪ የኢትዮጵያ ሕዝብ ልሳንነቱን እርግፍ አድርጎ በመተው የገዢው ፓርቲ አገልጋይ መሆኑን የትኛውም ኢትዮጵዊ የሚያውቀው ጉዳይ ነው፡፡ አንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ፕሮግራም ላይ በመላው አገሪቱ ሰላማዊ ሰልፍ እና ስብሰባዎችን በጠራበት ወቅት ኢቴቪ ጅሃዳዊ ሃረካት ፊልምን አቀናብሮ ፓርቲያችንን ከአሸባሪዎች ተርታ ሲፈርጀው ቆይቷል፡፡ ሌላው ቀርቶ ጉባኤያችንን ባከናወንበት ታህሳስ 19 ምሽት ኢቴቪ ያንኑ ፊልም በድጋሚ በማቅረብ አንድነት ፓርቲ በደሴ፣ በጎንደር፣ በአርባምንጭ፣ በጂንካ፣ በባህርዳር ወዘተ ካደረጋቸው ሰላማዊ ሰልፎችና በፓርላማ የፓርቲያችን ብቸኛው ተወካይ ስለ ፀረ ሽብር ህጉ አፋኝነት ያነሱትን ሀሳብ ከሽብር ጋር በማያያዝ ከንቱ ዲስኩር ሲያቀርብ ተመልክተናል፡፡ ኢቴቪ የአንድ ድርጅት መሆኑ አብቅቶ የኢትዮጵያን ሕዝብ ዋይታና ብሶት የሚያስተጋባ ግዙፍ የብዙሃን መገናኛ ድርጅት እንዲሆን አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡
7ኛ. ፓርቲያችን አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከተመሠረተበት ዕለት ጀምሮ ከኢህአዴግ አምባገነናዊ አገዛዝ ጋር በብርቱ እየተናነቀ መሪዎቹ እየታሰሩበትና እየተደበደቡበት መዋቅሩን በመላው አገሪቱ ዘርግቶ አመርቂ የትግል ውጤት እያመጣ ቢሆንም የኢትዮጵያን ሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት ለማረጋገጥ የሚቀረው ጉዞ እጅግ ረጅም ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ፓርቲያችን ይህ ታላቅ ጉባኤ የወሰናቸውን ውሳኔዎችና መርሃ ግብሮች በአግባቡ እየተወጣ ታሪክ ይሰራ ዘንድ አጥብቀን እናስገነዝባለን፡፡
በቀጣይ ዓመታት ፓርቲውን በበላይነት እንዲመሩ የተመረጡ አመራሮች ከመቼውም ግዜ በበለጠ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ከአደራ ጭምር እናሳስባለን፡፡


የለንደን ማርያም ቤ/ክ ጉዳይ፡ የሃሰተ መአትን በመርጨት እርስ በእርስ ለማጋጨት የሚጥሩ ካህናትን አሁንም ማርያም እያጋለጠቻቸው ትገኛለች

$
0
0

ቀን፡ 03/01/2014
በክህነት ካባ ተሸፍኖ እግዚአብሔን ሳይፈሩና ሰውን ሳያፍሩ የሃሰተ መአትን በሕዝበ ክርስቲያን ውስጥ በመርጨት እርስ በእርስ ለማጋጨት የሚጥሩ ካህናትን አሁንም ማርያም እያጋለጠቻቸው ትገኛለች።

አእምሮአቸውም በጠፋባቸው እውነትንም በተቀሙ እግዚአብሔርን መምሰል ማትረፊያ የሚሆን በመሰላቸው ሰዎች ይገኛሉ።እንደነዚህ ካሉት ራቅ።1ኛ ጤሞቲ.6፤4-6።

london
የቤተ ክርስቲያን አባላት፤ ካህናቱንና ምእመናኑን ወክለው ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንን በበላይነት እንዲያስተዳድሩ ሕዝብ መርጦ ሰይሟቸው የነበሩት 3 ካህናት፤ 4 ምእመናንና 1 የሰንበት ት/ቤት ተወካዮች የአገልግሎት ጊዜአቸውን ጨርሰው ለረጅም ጊዜ በኃላፊነት ላይ በመቆየታቸውና ከዛም ጋር ተያይዞ ብዙ የአስተዳደር ችግሮች በመከሰታቸው ምክንያት በ23 September 2012 ሁላችንም በገዛ ፍቃዳችን ከሥልጣናችን ለቀናል በማለት ለሕዝብ ይፋ አደረጉ።
ከዛም በመቀጠል አዲስ የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ ምርጫ ይካሄዳል ሲባል የካህናቱ ተወካዮች በተለይም አባ ግርማ ከበደ ሥላጣናቸውን ዘለዓለማዊ ለማድረግ ሲሉ አዲስ ምርጫ የሚካሄደው በሕዝቡ ፍላጎትና ውሳኔ ሳይሆን እኛ ባልነውና በሚመቸን መንገድ ብቻ ነው በማለታቸው ከፍተኛ ሁከት ተፈጠረ።
በዚህ ጊዜ ይህንን ሁከትና መከፋፈል መቋቋም ያቃታቸው 4ቱ የምእመናን ተወካዮች ቃላቸውን በመጠበቅ ሥራቸውን ሙሉ በሙሉ አቆመው እቤታቸው ቀሩ።
ይህ በሆነበት ወቅት አባ ግርማን ጨምሮ ሦስቱ ካህናት በምእመኑ መልቀቅ ተደስተው ሥልጣኑን ሁሉ የግላቸው በማድረግ የማይፈልጓቸውን የቤተ ክርስቲያኑን አባላት ቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ውስጥ እንዳትደርሱ በማለት በደብዳቤ ማገድና ማባረር በመጀመራቸው ቤተ ክርስቲያንን እስከማዘጋት የሚደርስ ሁከትና ረብሻ አስነሱ።

ከዛም በመቀጠል የቤተ ክርስቲያኑ መሰሶ፤ ጣሪያና ግድግዳ የሆኑትን አባላቱን ለማሸነፍ የሚችሉበትን ኃይል ለማግኘት ሲሉ የመረጣቸውንና የወከላቸውን ሕዝብ ከድተው ቤተ ክርስቲያኗ የሃገረ ስብከቱ ናት፤ ንብረቷም የቅዱስ ሲኖዶስ ነው የሚል ማጭበርበሪያን በመጠቀም የመንግሥት ተወካይ የሆኑ ጳጳሳትንና የኤምባሲ ባለሥልጣናትን ተጠቅመው ቤተ ክርስቲያኗን ከአባላቷ ነጥቀው በመውሰድ እጅ መንሺያና መሾሚያ መሸለሚያ ሊያደርጓት ጣሩ፤ ሆኖም ግን አባላት ባደረጉት ጠንካራ ትግልና በእግዚአብሔር ተራዳኢነት አንዱም ተንኮላቸውና ክህደታቸው ውጤት ሳያስገኝላቸው መክኖ ቀረ።
ከዛም በመቀጠል ቤተ ክርስቲያኗ የምትገኝበትን ሃገር አጠቃላይ ሕግና በተለይም ቤተ ክርስቲያኗ የተመዘገበችበትን የቻሪ ሕግ መከተልን አሻፈረኝ በማለት በማታለልና በመዋሸት የቤተ ክርስቲያንን ንብረት ከአባላቷ መንጠቅ እንችላለን በማለት የሃገርንም ሆነ የሕዝብ ንብረትን ሲዘርፉ ይሉኝታም ሆነ ሃፍረት ካልፈጠረባቸው የዘመናችን የቀን ጅቦች ጋር በመመሳጠር በቤተ ክርስቲያኑ አባላት ላይ የጥቃት ዘመቻ ከፍተው አሁንም በአባላቱ ጥንካሬና በእግዚአብሔር ተራዳኢነት የተኮል መረባቸው ሁሉ እንዳይሰራ ተደረገ፡፡
በመጨረሻ የቻሪቲ ኮሚሽን ጉዳዩን በመረዳት ምንም እንኳ ከሥልጣን አንለቅም ብለው ሥልጣንን የሙጥኝ ብለው ሕዝብንና ቤተ ክርስቲያንን የሁከት መድረክ ያደረጉት 4 የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አባላት (Trustees) ውስጥ አንድም ሥለ ምእመኑ የሚከራከርና ምእመኑን የሚወክል አባል ባይኖርም ከዚህ እነሱ የሙጥኝ ካሉት ሥልጣን እንደ ሰንኮፍ አውጥቶ በመጣል ቤተ ክርስቲያኗን እና አባላቷን ከፈጠሩባት ሕመም ለማዳን ያለው አማራጭ አዲስ ምርጫ ማካሄድ መሆኑን በመረዳት ባለ አደራዎች (Trustees) ነን ብላችሁ ከሆነ የምትንገታገቱት ኃላፊነት የሚሰማው ሥራ መሥራት አለባቸሁ በሚል በንፈስ መብታቸውን ለማስከበርና ቤተ ክርስቲያናቸውንና ሃይማኖታቸውን ጠብቀው ለማኖር ሕጋዊ መንገድ ይዘው ከሚታገሉ የቤተ ክርስቲያኑ አባላት ተወካዮችና የሕግ ጠበቃቸው ጋር ግንኙነት በመፍጠር ከቤተ ክርስቲያን መከፈት ጀምሮ አዲስ ምርጫ ስለሚካሄድበት ሁኔታ ታዛቢ ባለበትና፤ በፊርማ በሚረጋገጥ የውል ሰነድ መሰረት ስምምነትና መግባባት ላይ እንዲደርሱ ቀነ ገደብ ወስኖ መመሪያ ሰጣቸው።
ቻሪቲ ኮሚሽን ይህንን መመሪያ ሲያወጣ ግን እነሱ ብቻ ናቸው ትረስቲዎች ብሎ መወሰኑ ሳይሆን ማን ትረስቲ እንደሆነ የሚወስነው ፍርድ ቤት ነው በማለት ከችግሩ ለመውጣት ግን መፍትሔው ሁሉም ወገን የተስማማበት ምርጫ ማካሄድ ነው የሚለውን አበክሮ በመግለጽ ነበር።
ይህንንም ቻሪቲ ኮሚሽን በጻፈው ደብዳቤ በተራ ቁጥር 5 ላይ እንደሚከተለው በማለት ያብራራዋል።

“As part of our regulatory case we considered the question of who are the validly appointed trustees of the charity. This is a matter to which only the Courts can provide a definitive answer because the question centers on interpreting the governing document of the charity, which is under the jurisdiction of the Courts.”

ይህንን የመሰለ መመሪያና ማብራሪያ ቻሪቲ ኮሚሽን ለሁለቱም ወገን የሕግ ጠበቆች ልኮ እያለ የእውነትና የፍትሕ መንገድ ሁሉ ጨለማ መስሎ የሚታያቸው አባ ግርማና ተከታዮቻቸው ግን በተለመደው የቅጥፈት ተግባራቸው መሠረት ከመመሪያው ውስጥ ቻሪቲ ኮሚሽን ትረስቲዎች ናችሁ ብሎ ተቀብሎናል የሚል የተሳሳተ ትርጉም በማውጣት ከአሁን በኋላ የምንፈልገውን የፈላጭ ቆራጭነት ድርጊት ሁሉ የመፈጸም መብት ተሰጥቶናል የሚል አዋጅ አሰሙ።
ከዛም በመቀጠል
1. ረብሻና ሁከት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየተከሰተ በHealth & Safety ችግር ምክንያት ተዘጋ ብለው ለ9 ወር ያሸጉትን ቤተ ክርስቲያን የኛ ሥልጣን ተረጋግጦልናልና የቤተ ክርስቲያን አባላት ቢፈልጉ ገብተው ይጫረሱ በሚል የአረመኔነት መንፈስ ቤተ ክርስቲያኑ በ29/12/2013 እንከፍታለን የሚል ማስታወቂያ አሰራጩ።
London church
3. ከቄሱ የጳጳሱ እንዲሉ አቡነ እንጦስ የሚባሉ በኢትዮጵያ መንግሥት የዲፕሎማሲ ፓስፖርት የሚንቀሳቀሱና መንበራቸው በሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የሆነ፡ ራሷን ችላ ስትተድደር ከኖረችው ከንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌላቸው በሥላሴ ቤተ ክርስቲያንና በገብረኤል ቤተ ክርስቲያን በመገኘት ቤተ ክርስቲያኑን እንድከፍት ቻሪቲ ኮሚሽን ስለፈቀደልኝና ከቅዱስ ሲኖዶስም ስለታዘዝሁ እኔ አቅመ ደካማ ነኝና በ29/12/13 እሑድ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ድረሥ ሁላችሁም መጥታችሁ እንድትረዱኝ በማለት ስብከት፤ ቅስቀሳና ጥሪ አደረጉ። ከዛም በማያያዝ ከለንደን ውጪ ያሉ ተንቀሳቃሽ አብያተ ክርስቲያናት የመጓጓዣ ኮች ተልኮላቸው በነጻ በመጓጓዝ ማርያም ቤተ ክርስቲያን መጥተው የእነ አባ እንጦስ ሠራዊት ሆነው እንዲዘምቱ መርሃ ግብር ተዘጋጀ።
አቡነ እንጦስ ከአሁን በፊትም እንኳንስ ብጹዕ ከተባለ ጳጳስ ቀርቶ ከማንኛውም የእግዚአብሔር አማኝ ሰው በማይጠበቅ ሁኔታ የቤተ ክርስቲያኑ አባላት የሚጸልዩበት ቦታ ድረሥ በመምጣት ሰላም አወርዳለሁ በማለት እኔ የሁለታችሁም አባት ነኝ፤ ለአንዳችሁም አላደላም በማለት እውነተኛ አባት መንፈሳዊ አባት መሆናቸውን ለማሳየት ጥረው ነበር። የሚገርመው ግን ይህንን የቅጥፈት ቃል የሚናገሩት በሌላ በኩል ከቤተ ክርስቲያኗ አባላት ጋር ለውነት ቆመው የእውነት ሥራን በመስራት ላይ ያሉትን ቄስ ብርሃኑን ከቤተ ክርስቲያኑ አባላት ጎራ ወጥተህ ከኔ ጎን ተሰልፈህ አባላቱ እንዲበተኑ ካላደረግህ አሳርህን አሳይሃለሁ በማለት በስማቸው እየፈረሙ የሚልኩትን ከአንድም ሁለት የማስጠንቀቂያ ደብዳቤና ከአባ ግርማ ጎን ቆመው ቀን ከሌሊት እንደሚሰሩ እግዚአብሔር ቀርቶ አባላትም የሚያቁት የአደባባይ ምሥጢር ስለነበር እኝህ ጳጳስ እንኳንስ ሰውን እግዚአብሔርንም አታልላለው ብለው በማሰብ የሚያደርጉት ጥረት በእጅጉ የሚያሳዝንና የሚያሳዝን ነበር።
ይህ አልበቃ ብሏቸው ነው ዛሬ ደግሞ ሌላ በሬ ወለደ ሃሰት ለሕዝበ ክርስቲያኑ የሚነግሩት። አቡነ እንጦስ ቻሪቲ ኮሚሽን ቤተ ክርስቲያን እንድከፍት ፈቅዶልኛል ያሉት ቻሪቲ ኮሚሽን ግን የእሳቸው ጣልቃ መግባት ተገቢ ያልሆነ መሰናክል ነው በማለት የገለጸው ባጭሩ እንደሚከተለው ነበር።
“We have pointed out that a role of the Archbishop of the Diocese of North West Europe is neither appropriate nor desirable for the trustees to create unnecessary barriers to an inclusive election process.”
በሌላ በኩል ደግሞ አቡነ እንጦስ ይህንን የሃሰት መረጃ መሠረት በማድረግ ለጸሎትና ለቅዳሴ የተሰበሰበውን ሕዝበ ክርስቲያን እኔ አቅመ ደካማ ነኝና መጥታችሁ እርዱኝ ማለታቸው የቤተ ክርስቲያኑን በር ለመክፈት የሚፈነቅል ድንጋይና የሚጎተት ገመድ ኖሮ ጉልበት አስፈልጎ ሳይሆን በብዛት መጥታችሁ በቤተ ክርስቲያኑ አባላት ላይ በመዝመት ቤተ ክርስቲያኗን እንድወርስ እርዱኝ ማለታቸው ነበር።
በዚህ ድርጊታቸው እኚህ ጳጳስ ምን ያህል እግዚአብሔርን ሳይፈሩና ሰውን ሳያፍሩ ውሸትን ከመንዛት አልፈው ዓላማቸውን ለማሳካት ሲሉ አንዱን ክርስቲያን በሌላው ላይ አዝምቶ ማፋጀት የማያሳስባቸውና የማይጸጽታቸው ሰው እንደሆኑ መረዳት ይቻላል።
4. ከዚሁ ጋራ አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው፤ ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለሥልጣናት፤ የወያኔ የደህንነት ሰዎች፤ የሃገረ ስብከቱና የሥላሴ ሹማምንቶች ጋር በመሆን ለአካባቢው ፖሊስ ሥለ ቤተ ክርስቲያኑ አባላት የሃሰት መረጃንና ማስፈራሪያ በማቅረብ የፖሊስ ኃይል በተጋነነው መረጃ ላይ በመመርኮዝ ከፍተኛ የደም መፋሰስና መበጣበጥ ሊመጣ ነው ብሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ልዩ የፖሊስ ኃይል እንዲያሰማራ አስደረጉ።
5. አባ ግርማና ተከታዮቻቸው የሚደገፉት እጅግ ጥቂት በሆኑ አባላት በመሆኑና 90% የሚሆነው የቤተ ክርስቲያኑ አባላት አንባ ገነናዊና ክርስቲያናዊ ያልሆነውን ድርጊታቸውን የሚቃወምና የሚኮንን በመሆኑ፤ ቤተ ክርስቲያኑ ሲከፈት የወያኔ መንግሥት ደጋፊ የሆኑ የሥላሴና የገብረኤል ቤተ ክርስቲያን አባላት በተለይም የሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አባላት ከነካህናቱና የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አባላት (Trustees) ሳይቀሩ በዘመቻ መልክ መጥተው የቤተ ክርስቲያኑን አባላት በቁጥር በመብለጥ እንዲያጠቁላቸውና እንዲያባርሩላቸው በማሰብ የራሳቸውን ቤተ ክርስቲያን የቅዳሴ አገልግሎት በመጨረስ ተጓጉዘው እስኪደርሱላቸው ጊዜ እንደሚወስድ በማሰብ የቤተ ክርስቲያኑን መከፈቻ ሰዓት ከጠዋቱ 5 ሰዓት (1100) እንዲሆን አደረጉ።

የቤተ ክርስቲያኑ በሕገወጥ መንገድ መከፈት ከተረጋገጠ በኋላ የተፈጠሩ ክስተቶች።
1. የቤተ ክርስቲያኑ አባላት ቤተ ክርስቲያናቸው ከተዘጋችባቸው ጀምሮ ላለፉት 9 ወራት በብርድ፤ በዝናብና በቸነፈር ጸሎታቸውንና ልመናቸውን ሳያስተጓጉሉ በየዕለተ ሰንበቱ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ተኩል ጀምሮ ቤተ ክርስቲያናቸው በመድረስ በቅጥር ግቢ ውስጥ እስከ እኩለ ቀን ድረስ ጸሎትም ሆነ ሥርዓተ ቅዳሴ ያካሂዱ ሥለ ነበር በ29/12/13 በዛው መሠረት እቤተ ክርስቲያናቸው ቅጥር ግቢ ሲደርሱ አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው ከወያኔ ወኪሎችና ደጋፊዎች በሚያገኙት የገንዘብ ፈሰስ በመጠቀም ከፍተኛ ክፍያ የሚጠይቁ ከ10 ያላነሱ Private Security ቀጥረው በማቆም አባላቱ ወደ ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገቡባቸውን በሮች በሰንሰለት በመቆለፉ እንዲከለከሉ አደረጉ። ይህ የተደረገበት ምክንያትም አባላቱ የሌሎች ቤተ ክርስቲያን አባላት የራሳቸውን አገልግሎት ጨርሰው ተጓጉዘው ማርያም ቤተ ክርስቲያን እስኪደርሱና የአባ ግርማ ጎራ በሰው ኃይል እስኪጠናከር ጊዜ ለመግዛትና ከዚህም በተጨማሪ አባላቱ ለምን ማምለኪያና መጸለያ ቦታችንን እንከለከላለን ብለው አንባ ጓሮ እንዲፈጥሩና ይህ ሁኔታ ሲፈጠርም ፖሊስ ጠርቶ አባላትን ለማስያዝና ለማስወንጀል ነበር።
2. በዚህም ምክንያት ቤተ ክርስቲያኗን ከመመሥረት ጀምሮ ለደረሰችበት ከፍተኛ የዕድገት ደረጃ ለማብቃት ላለፉት 40 ዓመታት በጽናት ቆመው ሃብትና ጉልበታቸውን በማፍሰስ፤ የለፉ የደከሙና ያገለገሉ ካህናትና ምእመናን ከ1 ዓመት ህፃን ጀምሮ እስከ 80 ዓመት ዕድሜ ያላቸው አዛውንቶች፤ አቅመ ደካሞችና ህመምተኞች ሳይቀሩ በከፋው የክረምት ብርድና ቁር እየተጠበሱ አውራ ጎዳና አስፋልት ጫፍ ላይ በመኮልኮል ከሦስት ሰዓታት የበለጠ ቢሰቃዩም የደረሰባቸውን በደል ሁሉ በጽናትና በትዕግሥት በማለፍ ከፓሊስ ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር በመጨረሻ በፖሊስ ውሳኔና መመሪያ መሠረት የቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ በር ተከፍቶላቸው ሊገቡ ችለዋል።
3. እነዚህ በቁጥር ከ320 በላይ የሚሆኑ የቤተ ክርስቲያኑ አባላት ካህናትና ምእመናን ወደ ቅጥር ግቢው ሲገቡ አባ ግርማና ተከታዮቻቸው ተቻኩለው የቤተ ክርስቲያኑን ዋናና ትልቅ በር ብርግድ አድርገው ቢከፍቱም አባላቱ ግን የተከፈተው ቤተ ክርስቲያን መዝጊያ በር እንጂ የሰዎች በር እንደተዘጋና እንደተቆለፈ በመሆኑ በቤተ ክርስቲያን አባላት ላይ ቂምን ቋጥረው፤ ክርስቲያኑን ህብረተሰብ እርስ በእርሱ አጋጭተው በዛ መሃል ለመኖር ቀንና ሌሊት የዲያብሎስን ሥራ ከሚሰሩ ካህናት ጋር ሆዶ ሻክሮ ጥላቻን አዝሎ እርቅ ሳይወርድና ሰላም ሳይሰፍን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ መቀደስም ሆነ ማስቀደስ በእግዚአብሔር ማላገጥ ነው በሚል ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መግባትን ትተው ወደ ተለመደው የመቀደሻ ሥፍራቸው እየተዥጎደጎዱ ገቡ። ከዛም በመቀጥል ምንም ምንም ሳይሉ የዕለቱን ጸሎታቸውንና ሥርዓተ ቅዳሴ ማካሄድ ጀመሩ።
4. አባ ግርማና ተከታዮቻቸው፤ ከሥላሴ ቤተ ክርስቲያንና ከወያኔ ባለሥልጣናት ጋር በመሆን ከሌላ ቤተ ክርስቲያናትና ከለንደን ውጪ ያስመጧቸውን የወያኔ ደጋፊዎች በማግተለትል ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እንዲገቡ አደረጉ፤ እነዚህ አዋጅ ተነግሮና ነጋሪት ተጎስሞ የመጡ የወያኔ ደጋፊዎች ግን ሲበዙ ቢውሉ በቁጥር ከ120 የሚበልጡ አልነበሩም።
5. አቡነ እንጦስና የሃገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የተባለው መጋቢ ተወልደና ሌሎች የሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ሹማምንቶች የቤተ ክርስቲያኗ አባላት በአንጡራ ገንዛባቸው ገዝተው ባቆሙት የቪካሬጅ ህንፃ ውስጥ ሌሊቱን ተደብቀው በማንጋት በጓሮ በር አድርገው ከሕዝብ ተሸሽገው እንደ ሌባ በጓሮ በር ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ገቡ።
6. አባ ግርማና ተከታዮቻቸው ከቤተ ክርስቲያኑ መከፈት ጋር ያቀዱት ዕቅድና ያዘጋጁት ነገር ቢኖር በተቀደሰው የእግዚአብሔር ቤት፤ በጽላት ፊት ሕዝበ ክርስቲያንን ለማጋጨትና በሚነሳው ሁከት የቤተ ክርስቲያኑ አባላትን ወንጀለኛ አድርጎ በፓሊስ ለማስያዝ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በየ ጥጉ ካሜራና የድምጽ መቅጃ መሣሪያ አዘጋጅተው ልክ ወጥመድ ውስጥ እንደሚገባ አውሬ አባላትን መጠበቅ ነበር። እነሱ አባላትን ለማጥቃት ወጥመድ ቢያዘጋጁም በዛ ወጥመድ ውስጥ የሚገቡት ግን ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ተጠርተው በማያገባቸው የሌላ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ውስጥ ጣልቃ እንዲገቡ የተደረጉት ክርስቲያኖች ጭምር ሊሆኑ እንደሚችሉ ግን የእነ አባ ግርማ ጭንቅላት ታሳቢ እንደማያደርገው የታወቀ ነበር፤ ለዚህም ማረጋገጫው ከአሁን በፊት ወጣቶችን ከየቦታው ሰብስበው አባላትን ለጸብ እንዲያነሳሱና እንዲያስወነጅሉ፤ በመስደብና በድብቅ በመማታት እነሱ መልሰው እንዲመቷችሁ አድርጉ ብለው አሰማርተዋቸው አምስት ወጣቶች ሲታሰሩና ሲወነጀሉ እነ አባ ግርማን የተሰማቸው አንዳችም ፀፀት አልነበረም።
ይህንን ሁሉ ያገናዘቡትና አርቀው ያዩት የቤተ ክርስቲያኑ አባላት ቻሪቲ ኮሚሽን የሰጠው ሕጋዊና መመሪያ ተጥሶ ከአባላት ተወካዮችና ጠበቆች ጋር ፍጠሩ የተባሉትን line of communication ተግባራዊ ሳያደርጉ እነ አባ ግርማ ለሚፈጽሙት ሕገ ወጥ የተንኮል ተግባር ሰለባ ላለመሆንና ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በራሳቸውም ላይ ሆነ በሌሎች ክርስቲያን ወገኖቻቸው ላይ የሚደርሰውን ያልተገባ ነበር ለማስቀረት ሲሉ እነሱ እውጪ በብርድ እየተጠበሱ የሌላ ቤተ ክርስቲያን አባላት ቤተ ክርስቲያናቸውን ወረው ሲይዙ እያዩ ያቺን ቀን በታላቅ ትዕግሥትና ብልህነት አሳልፈዋታል፤ ነገም ቀን አለና የነገው ቀን ደግሞ ምን እንደሚሆን የሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ነው።

በመጨረሻም አባ ግርማ ከበደም ሆኑ ቄስ ዳዊት አበበና ቄስ አባተ ጎበና ሕዝብ አምኖና መርጦ የሰጣቸውን ጊዚያዊ ኃላፊነት ዘለዓለማዊ ለማድረግ ሲሉና የራሳቸውን ዓላማ ለማሳካት ሲሉ አንድ ሆኖ በኖረው ሕዝበ ክርስቲያን መካከል የሃሰት ክምር በመሥራት ሕዝብ እርስ በእርሱ እንዲከፋፈልና በጥላቻ እንዲተያይ ከማድረግ አልፈው የቤተ ክርስቲያኑን ውስጣዊ የአስተዳደር ችግር ወደ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት በማዛመት በሚያገኙት ድጋፍ የአባላትን መብት ለመጣስ የሚያደርጉት ጥረት በመጨረሻ በሕግ የሚያስጠይቃቸውና ምድራዊም ሆነ ሰማያዊ ፍርዳቸውን ከማግኘት እንደማይድኑ ማመንና መረዳት ያስፈልጋል።
ውድ የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላትና መላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮችና በ29/12/2013 በቤተ ክርስቲያናችሁ በመገኘት ቤተ ክርስቲያናችሁንና ሃይማኖታችሁን ለመጠበቅና መብታችሁን ለማስከበር በታላቅ ትዕግሥትና ችሎታ ዕለተ ቀኑ በሰላም እንዲያልፍ በማደረጋችሁ እግዚአብሔርም የሚወደው ሰላምና ትዕግሥትን ነውና የማያልቅበት አምላክ በረከቱን አብዝቶ ይሰጣችሁ! ያሰባችሁትን ሁሉ ያሳካላችሁ!!
ወደ ፊትም እንዲሁ በየ ዕለተ እሑዱና በአስፈላጊው ጊዜ ሁሉ ወደ ቤተ ክርስቲያናችሁ በመምጣት በዚህ የሕግ የበላይነት በሰፈነበትና የሰው ልጅ ነጻነት በተረጋገጠበት ሃገር የሃሰት ተግባርን፤ ተንኮልንና አንባ ገነንነትን በሕጋዊ መንገድ በመዋጋት ለቤተ ክርስቲያናችሁ፤ ለሃይማኖታችሁና ለመብታችሁ መከበር በጽናት በመቆም ሃሰትን በእውነት በማሸነፍ ሃይማኖታችሁንና ቤተ ክርስቲያናችሁን በመጠበቅ ለትውልድ የሚተላለፍ ስራ ታከናውኑ ዘንድ የእውነት አምላክና የእውነት መንገድ በሆነው በጌታችን በመድሐኒታችን በእየሱስ ክርስቶስ ሥም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር! አሜን!!
ለንደን ደብረ ጽዮን ቤተ ክርስቲያንን ከነጣቂዎች እናድን!!

በሞያሌ ከተማ የኦነግ ታጣቂዎች የፈጸሙትን ጥቃት ተከትሎ ከተማዋ በመከላከያ ሰራዊት ስትታመስ ዋለች

$
0
0

oLF Militeryኢሳት ቲቪ በዛሬ ስርጭቱ እንደዘገበው በሞያሌ ከተማ የኦነግ ታጣቂዎች የፈጸሙትን ጥቃት ተከትሎ ከተማዋ በመከላከያ ሰራዊት ስትታመስ ዋለች። ባለፈው ረቡእ ታጣቂዎቹ ከቀኑ 10 ሰአት ገደማ ወደ ከተማዋ በመግባት 3 ጠባቂዎችን በመግደልና አንደኛውን ታጣቂ መሳሪያውን በመቀማትና ልብሱን በማስወለቅ ” ሂድና ለአለቆችህ ንገር” በማለት ጉዳት ሳያደርሱበት መልቀቃቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል። ታጣቂዎቹ አንድ ድግን መትረጊስ፣ አንድ ላውንቸርና አንድ ባዙቃ ማርከው ወስደዋል። ይህንን ተከትሎ በአካባቢው የደረሱት የመከላከያ ሰራዊት አባላት አንዳንድ የከተማ ነዋሪዎችን እየደበደቡ ሲያሰቃዩ መቆየታቸውን ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ለኢሳት ገልጸዋል።

አንድ ሹፌር ለኢሳት እንደገለጹት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ተሳፋሪዎችን ከመኪና ላይ በማስወረድ ድብደባ እንደፈጸሙባቸውና እርሳቸውም በጥፊ እንደተመቱ ተናግረዋል
“እኛ ለምን እንደተደበደብን አልገባንም” የሚሉት ነዋሪዎች፣ ሁኔታው እስከትናንት ድረስ ውጥረት የነበረበት እንደነበርና ፍተሻው በእየጫካው እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

ታጣቂዎቹ በነዋሪዎች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለማድረሳቸውም ተገልጿል። በጉዳዩ ዙሪያ የሞያሌን አስተዳደር ለማነጋገር ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም። መንግስትም በጉዳዩ ላይ የሰጠው አስተያየት የለም።

ኦነግ ገዢውን ሀይል በትጥቅ ትግል ለማስወገድ ከሚንቀሳቀሱት ድርጅቶች መካከል አንዱ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ የመንግስት ታጣቂዎች በኦጋዴን ውስጥ በሚኖሩ ዜጎች ላይ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ኦጋዴን ፕሬስ ዘግቧል።

ልዩ ሚሊሺያ የሚባሉት ሀይሎች ከመከላከያ ሰራዊት አባላት ጋር በወሰዱት እርምጃ ፍሪህ ደሃግ አዳር የተባለው ሰው ሲገደል ሌሎች ደግሞ ቆስለዋል።

አቶ አያሌው ጎበዜ ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንትነታቸው ለምን ተነሱ?

$
0
0

ከአቡዛብር ተገኝ

ፋክት መፅሄት (በታህሳስ 2006፣ ቁጥር 26 እትሙ) የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ አያሌው ጎበዜ በምን ምክንያት ከስልጣን እንደ ተነሱ ያሰፈራቸውን መላምቶች አንብቤያለሁ፡፡ ብዙዎቹ በግምትና በይሆናል ላይ የተመሰረቱ ከመሆናቸውም በላይ ለግለሰቡ ከፕሬዝዳንትነት መነሳት በዋና ምክንያትነት ሊመደቡ የሚችሉ አይደሉም፡፡ ለዚህም ነው ለመፃፍ መነሳቴ፡፡

አቶ አያሌው ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንትነት የተነሱበት ዋና ምክንያት ምንድነው?

ከዜናው ሀሳብ በመነሳት በአንድምታ የምንረዳው እውነታ ስላለ፣ በኢቲቪ ከቀረበው የአቶ አያሌው ዱላ የማቀበል ዜና ልጀምር፡- በኢቲቪ ዜና መሰረት አቶ አያሌው ጎበዜ ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንትነት ስልጣናቸው የተነሱት በፍቃዳቸው ነው፤ “በቃኝ፣ ዱላውን ላቀብል” ብለው፡፡ እንኳንስ ከክልል ፕሬዝዳንትነት ስልጣን ላይ ይቅርና ከተራው የሹመት ስልጣን (ለምሳሌ ምክትል ቢሮ ሀላፊ፣ ከዚያም ዝቅ ሲል “ፕሮሰስ ኦውነር”) ላይ በራሱ ፈቃድ “ልውረድ” ያለን የፖለቲካ ተሿሚ፣ ኢህአዴግ “‘በቃኝ’ ካልክማ እሰዬ” ብሎ ቶሎ የመልቀቅ ልምድ የለውም፤ ኢህአዴግ እንደ ገብስ ቆሎ ሳያሽ የማውረድ ባህል የለውም፡፡ ኢህአዴግ፣ አፍ አውጥቶ “ሹሙኝ-ሹሙኝ” ያለን ወይም በጣም “በሚያስበላ” ሁኔታ እንዲሾም የቋመጠን ሰው የስልጣን መንበሩ የማያቀምሰውን ያህል፣ “ስልጣን በቃኝ” ያለን አባል፣ ተንደርድሮ አያወርድም – ለዚያውም የክልል ፕሬዝዳንት ያህልን ሰው፣ ለዚያውም አስቸኳይ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ ጠርቶ፡፡

አያሌው ጎበዜ

አያሌው ጎበዜ


ስለሆነም ኢቲቪ አቶ አያሌው ጎበዜ በራሳቸው ፈቃድ “የመተካካት መርሁ በ’ኔም ላይ ይተግበርልኝ” ብለው ከፕሬዝዳንትነታቸው ስለመልቀቃቸው የነገረን ዜና ታእማኒነት የሌለው፣ የተለመደ የኢህአዴግ ድራማ ለመሆኑ አንድ ማሳያ ነው፡፡ ሌላው ማሳያ ግለሰቡ አስቸኳይ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ ከስልጣን በለለቁበት እለት፣ ሙሉ አምባሳደር ሆነው የመሾማቸው “ትንግርት” ነው፡፡ የአማራው ክልል የምክር ቤት አስቸኳይ መደበኛ ስብሰባ የተጠራው፣ በአቶ አያሌው የቀረበውን “የመተካካት መርሁ በ’ኔም ላይ ይተግበርልኝ” ጥያቄ አዳምጦ ካመነበት ከፕሬዝዳንትነታቸው ሊያነሳቸው፣ ካላመነበት ደግሞ ጥያቄውን ውድቅ ሊያደርግ ነው፡፡ ወይም ደግሞ ጥያቄያቸውን በመሰረታዊ ሀሳብነት ተቀብሎ ከፕሬዝዳንትነታቸው የሚያነሳበትን ወቅት ግን የተወሰነ ጊዜ ሊያራዝም ይችላል፡፡

ከአምባሳደርነት ሹመታቸው የምንረዳው ግን ሁሉም ነገር ቀድሞ ያለቀ መሆኑን ነው፡፡ ግለሰቡ መነሳታቸውም፣ መሾማቸውም ያለቀ ነገር ነበር፡፡ መቼም ምክር ቤት ተብዬው የመወሰን ሙሉ ቀርቶ እንጥፍጣፊ ስልጣን እንኳን ቢኖረው፣ በአምባሳደርነት የተሾመን ግለሰብ ከፕሬዝዳንትነት ስለማውረድ፣ አለማውረድ ጉዳይ እንዲወያይ ባልተደረገ ነበር፡፡ በሌላ አነጋገር አቶ አያሌ ጎበዜ ከፕሬዝዳንትነታቸው እንዲነሱ ለምክር ቤቱ ሀሳባቸውን ካቀረቡበት እለት በፊት አምባሳደር ሆነው ተሹመዋል፡፡ ስለሆነም ቢያንስ በዚያች እለት ግለሰቡ ሁለት ጥምር ስልጣን በትከሻቸው ላይ ነበር – የአማራ ክልል ፕሬዝዳንትም፣ በቱርክ የኢትዮጵያ ሙሉ አምባሳደርም ነበሩ፡፡ ስለዚህም የአማራው ክልል ም/ቤት አስቸኳይ መደበኛ ስብሰባ ተጠርቶ ሲወያይ የነበረው፣ ቀድሞውኑ ከፕሬዝዳንትነቱ በተነሳና አምባሳደር ሆኖ በተሸመ ግለሰብ (አቶ አያሌው) ጉዳይ ላይ ነበር፡፡ (የኢህአዴግ ድራማ እንዴት ደስ ይላል¡)
ድራማው ግን በዚህ አያበቃም፡፡ አቶ አያሌው ለምን ከፕሬዝዳንትነታቸው እንዲነሱ ተደረገ? ፋክት መፅሄት ከተወሰኑ መላምቶች አንፃር በማየት ስለግለሰቡ አነሳስ ምክንያት ለማቅረብ ሞክራለች፡፡ ሆኖም አንዳንዶቹ መላምቶች የተሳሳቱና እጅግ የተጋነኑ ስለሆነ፣ እኔ ለክልሉ ባለስልጣናት ካለኝ ቅርበት አንፃር የተወሰኑት ላይ ማስተካካያ ለመስጠትና ለግለሰቡ ከስልጣን መነሳት ዋናውን ምክንያት ለመጠቆም እፈልጋለሁ፡፡

አቶ አያሌው ከስልጣን የተነሱት ለሱዳን ከተሰጠ የወሰን አካባቢ ቦታ ጋር የተያያዘ መሆኑን አንዳንድ ሰዎች ይናገራሉ፡፡ ከዚህ በፊትም አቶ አያሌው “አልፈርምም አለ” ተብሎ መናፈሱ ይታወቃል፡፡ ይህ ግን ስህተት ነው፡፡ አቶ አያሌ በዙሪያቸው ያሰባሰቧቸው የወንዝ ልጆች በስፋት የለቀቁት ተራ ፕሮፓጋናዳ ነው፡፡ አንደኛ መለስን እንኳንስ “የቁርጥ ቀን ልጅ” በሚፈለግበት እንዲህ ባለው ሁኔታ ቀርቶ፣ ቀላል በሚባሉት ጉዳዮችም “ይህን እኔ አልሰራም” የሚል ባለስልጣን ኢትዮጵያ አልነበራትም (ያማ ቢሆን ኖሮ፣ የተሸከምነው መከራ በግማሽ እንኳን በቀነሰልን ነበር)፡፡ እንዲያውም አቶ መለስ በአንድ ወቅት አቶ አያሌውን “አንተ የማትጠቅም፣ የማትጎዳም ነህ” ብለው በመተቸታቸው በድርጅቱ ትልልቆቹ አባላት ውስጥ ዜናው በስፋት ተናፍሶ ነበር፡፡ ባጭሩ አቶ አያሌው “እምቢ” የማለት ወኔው የላቸውም፡፡ (በሱዳኑ ፊርማ ላይ አቶ ደመቀ መኮንን እንዲሳተፉ የተደረገው፣ ሙስሊም ስለሆኑ/ኢስላማዊ ዳራ ስላላቸው የሱዳኖችን ስነልቦና “ለመግዛት” ኢህአዴግ የቀየሰው ስልት ከመሆን አይዘልም፣ ወደ አንዳንድ አረብ አገራት ዲፕሎማቶችን ሲመድብ ተመሳሳይ መንገድ ስለሚከተል፡፡)

እና አቶ አያሌው ለምን ከፕሬዝዳንትነታቸው እንዲነሱ ተደረገ? የአቶ አያሌው ከፕሬዝዳንትነት መነሳት ለብዙዎች ድንገታዊ ሊመስል ይችላል፤ አንደኛ አቶ አያሌው “የመተካካት መርሁ በ’ኔም ላይ ይተግበርልኝ” ብለው እንዲጠይቁና ይቺው ቃላቸውም ሳትጨመር-ሳትቀነስ በኢቲቪ እንድትተላለፍ ተደርጓል፡፡ ሁለተኛ “ከስልጣን አውርዱኝ” ጥያቆያቸውን ያየው ም/ቤት ጉዳዩን የተወያየበት በ“አስቸኳይ መደበኛ ስብሰባ” ነው፡፡ ሆኖም ግን ሀቁ ሌላነው፡፡ (እነዚህ ግርግሮች ሌላው የድራማው አካል ናቸው)፡፡

አቶ አያሌውን ከፕሬዝዳንትነት የስልጣን ኮርቻ የማንሳቱ እቅድ የተዘረጋው ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር (አቶ መለስ) በነበሩበት ወቅት ነው፡፡ አቶ መለስ በመሩትና ባህር ዳር ላይ በተካሄደ የኢህአዴግ ስብሰባ ላይ አቶ አያሌ ተገምግመዋል፡፡ በዋናነት የቀረበባቸውና የተቀበሉት ክስም በክልሉ ባሉ የተለያዩ የስልጣን/የሹመት እርከኖች ላይ የራሳቸውን አካባቢ ሰዎች እጅግ በተደራጀ መንገድ ማሰባሰባቸው ነው፡፡ አንዳንዶች ሂደቱን “ጎጃማይዜሽን” ይሉታል፤ ሌሎች ደግሞ “ማርቆሳይዜሽን” በማለት ይጠሩታል፡፡

አቶ አያሌው ሹመት የሚሰጡበት ቀመር በጣም ግልፅ ነው፡፡ እሳቸው ከመጡበት ከደብረ ማርቆስና አካባቢው የተማረ ከተገኘ ያለ ምንም ጥርጥር ይሾማል፡፡ ማርቆሴ እያለ ሌላ ሰው በምንም ሁኔታ አይሾምም፡፡ ማርቆሴ ከጠፋ፣ የአቶ አያሌው ሁለተኛው የሹመት ቀመር ስራ ላይ ይውላል፤ ጎጃሜ የሆነ ሰው ተፈልጎ ይሾማል፡፡ ማርቆሴ ሁሉ ጎጃሜ ቢሆንም፣ ጎጃሜ ሁሉ ግን ማርቆሴ አይደለም፡፡ ሆኖም ማርቆሴ ያልሆነ ጎጃሜን መሾም፣ ጎንደሬን፣ ወሎዬን ወይም የሰሜን ሸዋ ሰው ከመሾም እጅግ የተሻለ ነው፤ ምክንያቱም ጎንደሬም፣ የሸዋ ሰውም ሆነ ወሎዬ መቼም ቢሆን ጎጃሜ አይደለምና፡፡ ይህ የአቶ አያሌው የሹመት ቀመር ከስልጣን በሚወርዲት ላይም ስራ ላይ ይውላል፤ ባብዛኛው ከስልጣን የሚወርድ ተሿሚ ማርቆሴ ወይም ጎጃሜ አይደለም፤ ባጋጣሚ ነገሩ ከፍቶ ከስልጣን ከተነሳም ወይ የተሻለ ቦታ ይሰጠዋል፤ ካልሆነም በያዘው ደረጃና ደመወዝ የአቶ አያሌው አማካሪ ሆኖ ይሾማል (ፉገራ በሚወዱ ካድሬዎች አነጋገር Recycle Bin ውስጥ ይገባል፡፡ ይህ ማለት እንደ ገና የሚሾምበት ጊዜ አለ ማለት ነው፤ አቶ አያሌው ማዘናጋት የሚገባቸውን ካዘናጉ በኋላ፡፡ የቀመሩን ዘረኝነት (racist) ልብ ይሏል፡፡)

ይህም በመሆኑ አሁን በአማራ ክልል ርእሰ ከተማ -በባህር ዳር- ብዙዎቹን የመንግስት ተቋማት የሚመሩት ባለስልጣኖችና ምክትሎቻቸው፣ ዝቅ ሲልም የምክትሎቹ ምክትሎች (ፕሮሰስ ኦውነር፣ መምሪያ ሀላፊ፣ ወዘተ) በዚህ የአቶ አያሌው የሹመት አሰጣጥ ቀመር ወደ ስልጣን የመጡ ናቸው፡፡ ይህ የአቶ አያሌ የሹመት ቀመር በቀጥታ በማይመሩት በባህር ዩኒቨርስቲ ጭምር ስራ ላይ እየዋለ እንደ ሆነ ይነገራል፤ ዩኒቨርስቲው በፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር የሚመራና ያሉት መምህራንም ከአገሪቱ ብሄር ብሄረሰቦች የተገኙ ሆነው እያለ፤ የፕሬዝዳንት፣ ምክትል ፕሬዝዳንቶችና ዲን ስልጣን (ወረድ ሲልም ከፕሮግራም ሀላፊ) በአብዛኛው በመጀመሪያ ደረጃ በማርቆሴዎች፣ ከዚያም በጎጃሜዎች “ቡድን” እንዲያዝ ተደርጓል፡፡ የአቶ አያሌው የጎጠኝነትና የዘረኝነት እጅ ይሄን ያህል ረጅም ነው፡፡

ይህ ድርጊታቸው ማለትም ክልሉን የጎጠኞች አምባ ማድረጋቸው አቶ አያሌውን ክፉኛ አስገምግሟቸዋል – በአቶ መለስና በሌሎቹም የኢህአዴግ ቁንጮ አባላት፡፡ ሆኖም አቶ መለስ በሀይል የወቀሷቸውን፣ የሰደቧቸውን፣ ያንቋሸሿቸውን ያህል አቶ አያሌውን ሮጥ ብለው ከስልጥን ማንሳት አልሆነላቸውም፡፡ በአቶ አያሌው ድርጊት “የበገኑትን” ያህል የይስሙላውን የአማራ ክልል ም/ቤት አስቸኳይ መደበኛ ስብሰባ አስጠርተው ግለሰቡን ከፕሬዝዳንትነታቸው በማስወረድ “የትምህን ግባ” ማለት አልቻሉም፡፡ ያን የመሰለ ባለ ራእይ መሪ ይህን ማድረግ ለምን ተሳነው?
ምክንያቱ ግልፅ ነው፡፡ አቶ አያሌው ዙሪያቸውን ያሰለፉት የጎጥ ሀይል ቀላል አይደለም፡፡ ከላይኛው የክልል ካቢኔ ጀምሮ፣ የቢሮ ሀላፊዎች፣ ምክትሎቻቸው፣ ከምክትሎቹ ስር ያሉ ሌሎች ሀላፊዎች ከ95 በመቶ በላይ ከፍ ሲል የተገለፀውን የአቶ አያሌውን የሹመት ቀመር ተከትለው የመጡ ናቸው፡፡ (እዚህ ላይ ከምክትል ቢሮ ሀላፊዎች በታች ባለ የስልጣን ሹመት ላይ አቶ አያሌ ቀጥተኛ ሚና የላቸውም፡፡ ሆኖም በሹመት ቀመራቸው ያመጧቸውን የራሳቸውን የወንዝ ልጆች በሳቸው ቀመር እንዲመሩ ማድረግ አይሳናቸውም፤ አድርገውታልም፤ ተገምግመውበታልም፡፡)
ስለሆነም አቶ አያሌውን በድንገት እንደ ሙጀሌ ፍንቅል ማድረግ አደጋ እንዳለው ኢህአዴግ አመነበት፡፡ እዚያ ክልል ላይ የሰፈረውን አብዛኛውን ባለስልጣን አስኮርፎ ክልሉን መምራት (እንደፈለጉ ማሽከርከር) እንደማይቻል ኢህአዴግ ልብ አለ፡፡ ምናልባት ቅሬታው ስር ሰዶ በተለይም ደብረ ማርቆስ ወደሚገኘው ህዝብ ሊደርስና ያልተፈለገ መነሳነሳት/ብጥብጥ ሊያስከትል እንደሚችል እነመለስ ሰጉ፡፡ ስለሆነም ግለሰቡን በረጅም ጊዜ ለማውረድ መስራት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ሆነ፡፡

እናም በክልሉ መስተዳድር መዋቅር ውስጥ የሌለ አደረጃጀት ኢህአዴግ ፈጠረና ከፕሬዝዳንቱ ሰር ሁለት ምክትሎች እንዲኖሩ ተደረገ፡፡ ሁለቱ ምክትሎችም በአቶ አያሌው ዙሪያ ካሰፈሰፉት የጎጥ ቡድኖች ውጭ እንዲሆኑ ተደረገ፤ አቶ አህመድ አብተውና አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ሁለት ምክትል ፕሬዝዳንቶች ሆነው ተሸሙ፤ ሁለቱም ከወሎ፡፡ ስለሆነም አቶ አያሌው የነበራቸው ያሹትን የማድረግ ስልጣን በእጅጉ ተገድበ፤ ባጭሩ ተንሳፈፉ፡፡

የተዘረጋውን ጠንካራ የማርቆሴ መዋቅርና የአቶ አያሌውን ተፅእኖ የማዳከሙ ስራ እንደ ተሳካ ሲታወቅ የይስሙላው የአማራ ክልል ም/ቤት ተጠራ፤ የይስሙላውን የአቶ አያሌው ዱላ ላቀብል የሚል ምክንያት አዳመጠ፤ አፅድቅ የተባለውን አፀደቀ፡፡ በቃ- የሆነው ይኼው ነው፡፡
በነገራችን ላይ ኢቲቪ በአንድ የዜና ስርጭት ላይ፣ የአቶ አያሌውን ከስልጣን መውረድ “ካረዳ” በኋላ፣ ወዲያው በማስከተል በሙሉ አምባሳደርነት መሾማቸውን “ማብሰሩ” ሰውዬው ከፕሬዝዳንትነት በመነሳቱ ቅር የሚላቸውን መገኖች (የማርቆሴ ቡድን) ስሜት ለማከም መሆኑን ልብ ይሏል፤ ኢህአዴግ እንዲህ ነው መፍራት ሲጀምር ልክ የለውም፣ መድፈር ሲያበዛ ልክ እንደሌለው ሁሉ፡፡

ሌላው ለአቶ አያሌው ከስልጣን መሳነት እንደ ተጨማሪ ምክንያት ሊቀርብ የሚችለው፣ የምስራቅ ጎጃም በተለይም በሞጣ የአዲስ አበባ መንገድ አቅጣጫ ያለው ህዝብ ተደጋጋሚ ቅሬታና አቤቱታ ነው፡፡ የአዲስአበባ-ሞጣ-ባህር ዳር የጠጠር መንገድ በአስፋልት እንዲሰራ የአካባቢው ህዝብ ለዘመናት ጠያቄ ሲያቅርብ ኖሯል፡፡ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር – አቶ መለስ – ለህዝቡ ቃል የገቡ ቢሆነም እስካሁን ድረስ የመንገድ ስራው ሊጀመር አልቻለም፡፡ ለዚህ ደግሞ ዋናው ተጠያቂ፣ የአካባቢው ህዝብ እንደሚናገረው፣ አቶ አያሌው ናቸው፤ “አቶ አያሌው በስልጣን እያለ የኛ መንገድ አይሰራም” በማለት ቅሬታቸውን በምሬት ይናገራሉ፡፡ በቅርቡ ሰላማዊ ሰልፍ ሁሉ ወጥተዋል፡፡ ግን አቶ አያሌው ለምን ችክ ብለው መንገድ ግንባታውን ያሰናክላሉ?

የአካባቢው ተወላጅ ምሁራን እንደሚሉት የሞጣው መንገድ መሰራት ከአዲስ አበባ-ባህር ዳር ያለውን ርቀት ቢያንስ በ70 ኪሎ ሜትር ስለሚያሳጥረው፣ በነባሩ መስመር ማለትም በቡሬ በኩል ባሉት ከተሞች ላይ ከፍተኛ የሆነ አሉታዊ ተፅኖ ይኖረዋል፤ ያለ ጥርጥር ብዙዎቹ ተሸከርካሪዎች በሞጣው መስመር ስለሚሄዱ የቡሬ መስመር ነጋዴዎች በተለይም ሆቴሎች ገቢ ትርጉም ባለው ሁኔታ ማሽቆልቆሉ አይቀሬ ነው፡፡ ደብረ ማርቆስ ያለችው ደግሞ በዚሁ የቡሬ መስመር ነው፡፡ አቶ አያሌው ደግሞ ከዚህች አካባቢ ምሁራን ብቻ ሳይሆን ከከተማዋ ጋር ያላቸው ፍቅር ወደር የለውም፡፡ እናም ለጎጣቸው ሲሉ የጎረቤታቸውን ጎጥ መልማት ሲከላከሉ ነው የኖሩት፡፡
እና ኢህአዴግ እኒህን ሰው ከስልጣን ማንሳት ይነሰው?

የሰላማዊ ትግል እድገታችን –ግርማ ሞገስ

$
0
0
(ግርማ ሞገስ)

(ግርማ ሞገስ)

የዚህ ጽሑፍ ግብ የሰላማዊ ትግል እድገት ከኢትዮጵያ ውጭ እና በኢትዮጵያ ውስጥ ያደረጋቸውን እድገቶች ታሪክ ማጥናት ነው።
(ሀ) ከኢትዮጵያ ውጭ፥
(1) ከክርስቶስ መወለድ ቀደም ብሎ
ጥንታዊ ሮማውያን ከክርስቶስ ልደት 509 አመቶች ግድም ቀደም ብሎ የነበረውን ፍጹም አምባገነናዊ የዙፋን አገዛዝ አፍርሰው ረፓብሊክ የፖለቲካ ስርዓት መሰረቱ። ይህ አዲስ ህብረተሰብ ፓትሪሳን (Patrician) እና ፕሌቢያን (Plebeian) በሚባሉ ሁለት መደቦች የተከፈለ ነበር። ፓትሪሳን የሚባለው መደብ በቀድሞው ንጉሳዊ ስርዓት የነገስታት እና የባላባት ዝርያዎችን የነበሩትን ያካተተ የገዢዎች መደብ ነበር። ፕሌቢያን (Plebeian) የተባለው መደብ አናጺውን፣ ብረታ ብረት አቅላጩን፣ መንገድ እና ህንጻ ሰራተኛውን፣ አራሹን፣ ነጋዴውን፣ ምግብ አብሳዩን፣ በወታደርነት አገልጋዩን እና የመሳሰለውን የህብረተሰብ ክፍል ያካተተ መደብ ነበር። -–ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ–-

 

እስር ላይ የሚገኘው አንዷለም አራጌ አዲሱን የአንድነት አመራር “ሕዝቡን ለመብቱ እንዲታገል አንቁት”አላቸው

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ዘንድ የ2005 ዓ.ም የዓመቱ ምርጥ ሰው ሽልማትን ያገኘውና በ እድሜ ልክ እስራት በገዢው መንግስት ተበይኖበት ቃሊቲ የሚገኘው አንዷለም አራጌ ዛሬ ጠዋት ሊጠይቁት የሄዱትን አዳዲሶቹን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች “ሕዝቡን ለመብቱ እንዲታገል አንቁት፤ ሕዝቡ መብቱን አውቆ ለመብቱ እንዲነሳ በማንቃት ለውጥ ለማምጣት ጠንክራችሁ ሥሩ፤ እንደምታደርጉትም ተስፋ አለኝ” ማለቱን ከአዲስ አበባ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ገልጸዋል።
Andualem aragie
ባሳለፍነው ሳምንት የፕሬዚዳንት ነጋሶ ጊዳዳን እና ካቢኔያቸውን በምርጫ አሰናብቶ በአዲስ የሾመው አንድነት ፓርቲ፤ አዳዲሶቹ ተሿሚዎች ስልጣናቸውን ከተቀበሉ በኋላ የመጀመሪያ ሥራቸውን ያደረጉት በ እስር ቤት የሚገኙትን የፓርቲዎቻቸውን አባላት መጠየቅ ነበር። በዚህም መሠረት አዳዲሱ አመራር እስር ቤት ከሚገኙት የድርጅቱ አመራሮችና አባላት የሚያበረታቱ ምክሮችን መቀበሉን ከዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ዘገባ ለመረዳት ተችሏል።

አንዷለም አራጌ በአዲሱና በወጣት በተገነባው የአንድነት ፓርቲ አመራር ደስተኛ መሆኑን ገልጾ “ሕዝቡን ለመብቱ እንዲታገል አንቁት፤ ሕዝቡ መብቱን አውቆ ለመብቱ እንዲነሳ በማንቃት ለውጥ ለማምጣት ጠንክራችሁ ሥሩ፤ እንደምታደርጉትም ተስፋ አለኝ” ብሏቸዋል። ይኸው የአንድነት ፓርቲ አመራር እዛው ቃሊቲ የሚገኙትን እነ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ጨምሮ ሌሎች የሕሊና እስረኞችን ለመጠየቅ ጠይቆ መከልከሉ የታወቀ ሲሆን ወደ ዘዋይ ያመራው የአንድነት ፓርቲ ቡድን እዛው እስር ቤት የሚገኙትን ን የአንድነት የብሄራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ናትናኤል መኮንንና በዚያ የሚገኙ ሌሎች እስረኞችን መጎብኘታቸውም ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በሕወሓት/ ኢሕአዴግ አስተዳደር “በሽብርተኝነት ወንጀል” ተከሷል፤ በሌሎች ኢትዮጵያውያን ዘንድ ደግሞ የሕሊና እስረኛ ነው የሚባለው አንዷለም አራጌ ከዚህ ቀደም ከ እስር ቤት ተቃዋሚዎች የእኔን እስር ቤት መማቀቅ ልትጠቀሙበት አልቻላችሁም፤ ሕዝቡን ለማታገል ልትጠቀሙበት ትችሉ ነበር ሲሉ የነበረውን ድክመት መግለጹን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም።

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live