Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

Hiber Radio: መንግስት አገሪቱን እየመራ ነው ማለት እንደማይቻል ተገለጸ፣ ሕዝቡ ተቃውሞውን አስተባብሮ ዳር የሚያደርስ መሪ ማጣቱ ተገለጸ

$
0
0

Habitamu<በአሁኑ ወቅት በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ላይ ስርዓቱ በራሱ ሕገ መንግስት እንኳ የተፈቀደውን አማራ ነን ስላሉ የተፈጸመውን ግፍ እዚህ ቦታው ተገኝቼ ስሰማ በእውነት ይህ ሁሉ ግፍ የሚፈጸመው ለምንድነው? የወልቃይትን ትግል ያስተባብራሉ ያሉ ተገለዋል፣ታስረዋል፣ታፍነው ተወስደዋል፣በሱዳን ወታደሮች እንዲገደሉ ተደርገዋል፣በርካታ ሴቶች በአንድ ወንድ ተደፍረዋል ሌላም ብዙ ግፍ ተፈጽማል። የሚታየው ስርዓቱ ይህንን የሕዝብ ጥያቄ መመለስ ካልቻለ ጸቡ ከወልቃይት ብቻ ሳይሆን ከመላው አማራ ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ጋር ነው…የኦሮሞ ወገኑ እየተገደለ ሌላው ሁኔታውን ለምን ቁጭ ብሎ ያያል የሚለው በፊት ግራ አጋብቶኝ ነበር አሁን ግን ግራ አያጋባኝም። …በአሁን ሰኣት ተቃውሞና ችግር ኦሮሚያ ላይ ብቻ አይደለም ችግር የሌለበት ቦታ የለም።መንግስት የትን ነው የሚያስተዳድረው አዲስ አበባን ብቻ? ሕዝቡ ተበታተነውን ተቃውሞ በአንድ ላይ የሚአስተባብረው መሪ ይፈልጋል ተቃውሞው መሪ የለውም ሕዝቡ ነው በራሱ በቃኝ ብሎ እየመራ ያለው…>

ጋዜጠኛ ሙሉቀን ተስፋው የቀለም ቀንድ ዋና አዘጋጅ ከአገር ቤት ለህብር ሬዲዮ ከሰጠው ሰፋ ያለ ቃለ ምልልስ የተወሰደ(ሙሉውን አዳምጡት)

<…ዶ/ር ማይ ገነት ለሴቶች መብት ተቆርቋሪ.ለሰብዓዊ መብት ተማጋች ብቻ አይደለችም በአጠቃላይ ለማህበረሰቡ ተቆርቋሪ ነጭ። ሴቶች ወደ አመራር እንዲመጡ ብዙ ደክማለች…> ወ/ሮ ወሰንለሽ ደበላ የቀድሞ የኢትዮጵያ ሴቶች መብት ማዕከል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ስለ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቿ እና ባለፈው ሳምንት ከዚህ ዓለም በሞት ስለተለየችው ዶ/ር ማይገነት ከተናገረችው(ቃለ መጠይቁን ያዳምጡት)

<…እነ አበበ ቢቂላ ፣ማሞ ወልዴ፣ፋጡማ ሮባ፣ደራርቱ ቱሉ፣ምሩጽ፣የዲባባ ልጆች፣እነ ሀይሌ ፣ቀነኒሳና ሌሎቹምአገራቸውን በክብር እንዳላስጠሩ ዛሬ አበረታች እጽ በመውሰድ ስማቸው የሚጠራ አትሌቶች መኖራቸው ያሳፍራል በአንድ በመንደር ልጆች የተያዘው ስልጣንን ተገን ያደረገው ባለሙያ አልባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ይፍረስ..>

/ ውስጥ በገሃድ ሲሸጥ ከርሞ ለእውቅ እና ለብርቅዩ አትለቶቻችን እንቅፋት የሆነው በአለም ላይየታገደው ጉልበት ሰጪ መድሐኒት ያሰከተለው በሔራዊ እና አለማቀፋዊ መዘዝ ሲዳሰስ ልዩ ዘገባው የተወሰደ ሙሉውን ያዳምጡት

የአሜሪካ አከራካሪና አስተዛዛቢ አቋም በአጼ ሀይለስላሴ፣በደርግና በወያኔ ዘመን ከኤርትራ መገንጠል በፊትና በሁዋላ ዲፕሎማሲዋና ድጋፉዋና ማዘናጊያዋ የቀድሞ ዲፖሎማቶቿ ምስክርነት ሲፈተሽ(ልዩ ዘገባ )

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

መንግስት አገሪቱን እየመራ ነው ማለት እንደማይቻል ተገለጸ

ሕዝቡ ተቃውሞውን አስተባብሮ ዳር የሚያደርስ መሪ ይፈልጋል አማራጭ አጥቶ በራሱ እየተመራ ነው ተባለ

በወልቃይት ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ ካላቆመ ሁኔታው ወደ አደገኛ አቅጣጫ ሊቀየር ይችላል ተብሏል

ግብጾች በአባይ ጉዳይ ዛሬም ከፍተኛ ስጋት እንዳላቸው ተገለጸ

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በኦሮሚያ ለተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞ የሀይል አማራጭና በኦህዴድ ላይ የተያዘው ሹም ሽር ውጤት እንደማያመጣ ገለጹ

በአዲስ አበባ በሆስኒ ሙባረክ ላይ ግድያ ያሴሩት የሱዳኑ አል ቱራቢ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ድሪም ላይነር አውሮፕላን አዲስ አበባ ላይ እንግዳ የሆነ ሰው ሰራሽ ችግር ገጠመው

ከአደጋው ጋር በተያያዘ አንድ የአየር መንገዱ ሰራተኛ ጉዳት አግኝቷቸዋል ተብሏል

ሱዳን ወደ ኤርትራ ታፍነው የተወሰዱ ኢትዮጵያዊያን ታጋቾችን ለማስለቀቅ የገላጋይነት ሚና መጫወቷ ተነገረ

ፓርላማው አጠገብ የሚገኘው በፌዴራል ፖሊስ ጠዋት ማታ የሚጠበቀው የፌዴሬሽን ም/ቤት መጋዘን መዘረፍ አነጋጋሪ ሆነ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ


Health: የስኬታማ አመራሮች 5 የውጤት ምስጢራዊ ባህሪያት

$
0
0

152

ለአንድ ተቋም የላቀ ውጤታማነት ትልቁን ሚና የሚይዘው አመራሩ ነው፡፡ የአመራሩ ጥንካሬ ወይም ድክመት አንድን ትንሽ ተቋም አይደለም አገርን ያህል ነገር ደካማ ወይም ጠንካራ ሊያደርግ ይችላል፡፡ በተለያዩ ተቋማት ውስጥ ያሉ አመራሮች የሚመሩት ድርጅት አትራፊም ይሁን ትርፋማ ያልሆነ እስከ 40 በመቶ ድረስ ውጤታማነቱን የመወሰን አቅም አላቸው፡፡ አመራሩ የበታች ሰራተኞችን ይቀጥራል፣ ያሰራል፡፡ ድርጅቱ ውጤታማ ባይሆን ተጠያቂው የሚሆነው ስራውን በበላይነት የሚያሰራው ወይም ደግሞ ስራውን የሚሰሩ ሰዎችን የቀጠረው ነው ሊሆን የሚችለው፡፡ ለዚያም ነው አንድ ድርጅት ሲመሰረት አመራሩ ማነው ተብሎ በቅድሚያ መለየት ያለበት፡፡
የምንመራው ተቋም የፖለቲካ ፓርቲ ሊሆን ይችላል፣ የእግር ኳስ ክለብ ሊሆን ይችላል፣ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅትም እንዲሁ፡፡ በተመሳሳይ መልኩ አትራፊ የንግድ ድርጅትም ሊሆን ይችላል፡፡ ሁሉም እንደ ተቋም ግን የተቋቋመበትና ሊያሳኩት የሚፈልጉት ራዕይና ግብ አላቸው፡፡ ተቋምን ተቋም ከሚያሰኙት አንዱ መለያ ባህሪያቸው ሰርቶ ሊያሳካቸው የሚፈልጋቸው ግልፅ አላማዎች መኖራቸው ነው፡፡ እነዚህን ዳር ለማድረስ ነው እንግዲህ የአመራሩ ሚና፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ የምርጥ አመራር ባህሪያት ምንድን ናቸው?
አንድ አመራር ብቃት የ‹‹BASKET›› ፅንሰ ሃሳብን ያሟላ መሆን አለበት፡፡ ሁሉም ሰው መሪ መሆን ቢፈልግም መሪ መሆን የሚችሉት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው፡፡ መሪ መሆን ችለውም የላቀ ውጤት ማስመዝገብ የሚችሉት አሁንም ጥቂቶች ናቸው፡፡ የእጅግ ውጤታማ ሰዎች አመራሮች አንድ መገለጫዎች ‹‹BASKET›› የተባለውን መስፈርት የሚያሟሉ መሆናቸው ነው፡፡  ‹‹ባስኬት›› ሲባል ቅርጫት ለማለት ተፈልጎ አይደለም፡፡ ምህፃረ ቃል ነው፡፡
1. B- Behavior…ባህሪ!
“Leadership is a potent combination of strategy and behavior. But if you must be without one, be without strategy”… Norman Skhwarzkopf
እንደሚታወቀው አንድ አመራር ስለሚጠበቅበት የስራ ኃላፊነት ሊወጣው የሚያስችለው ባህሪ ሊኖረው ይገባል፡፡ አንዳንዱ መሪ እንኳን ለመምራት ለመመራት የማይሆን ባህሪ ያለው አለ፡፡ እንኳን ሌሎችን ሊመራ ራሱ መሪ የሚያስፈልገው ሰውም አለ፡፡ የመሪነት ባህሪ ራሱን የቻለ ልዩ ገጽታ ነው፡፡ ለዚያም ነው ሁሉም ሰው መሪ መሆን የማይችለው፡፡ ለዚያ ኃላፊነት ዝግጁ የሆነ ባህሪ ሊኖረው ይገባል፡፡ አንድ ሰው በአገራችን ካለው የሊደርሽፕ ተቋምም ሆነ ሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ ቢማር የመሪነት ባህሪ ካልታደለው ወይም ደግሞ በውስጡ ካላዳበረው ውጤታማ መሪ ሊሆን አይችልም፡፡
መኪና ከፈለግንበት ቦታ ሊያደርሰን የሚችለው ጎማ ሲገጠምለት ነው፡፡ አንድ መሪም እንዲሁ የሚመራውን ተቋም ከዳር ማድረስ የሚችለው ለአመራርነት የሚያበቃ ባህሪ ሲገጠምለት ነው፡፡ ከየትኛውም ተቋም ውጤት በስተጀርባ የአመራሮችን ባህሪ እናገኛለን፡፡ ጥሩ ውጤት ያላቸው ከሆነ ጥሩ የአመራር ባህሪ አላቸው ማለት ሲሆን ውጡቱ ደግሞ ከተጠበቀው በታች ከሆነም ባህሪያቸው የዚያኑ ያህል ሆኗል ማለት ይቻላል፡፡
አንድ የእግርኳስ አሰልጣኝ ለአሰልጣኝነት የሚሆን ባህሪ ከሌለው ቡድኑ ውጤት ሊያመጣ አይችልም፡፡ አንድ የፖለቲካ ተቋም /ፓርቲ/ መሪ ፖለቲካዊ መድረክን ወደ ውጤት ለመቀየር የሚያስችል አፈፃፀም ከሌለው በተመሳሳይ መልኩ ፓርቲው እንኳን ምርጫ ተወዳድሮ ሊያሸንፍ አይደለም የራሱን ህልውና ለማስጠበቅ እንኳን ሊሳነው ይችላል፡፡ አንድ የንግድ ተቋም አመራር ለንግድ አመራርነት የሚያበቃ ባህሪ ከሌለው ድርጅቱ አትራፊ ሆኖ ሊዘልቅ አይችልም፡፡ ይህ የሚያሳየን የአመራር ባህሪ እንደየተቋሙ ባህሪ የሚለያይ መሆኑ ነው፡፡
ለዚያም ነው ታክሲ ሲነዳ የነበረ ሹፌር አውቶብሱን መንዳት የሚሳነው፡፡ አውቶብሱን ለመንዳት የሚያስችል ባህሪ ከዳበረ ግን በጥሩ ሁኔታ መንዳት ይችላል፡፡ አንድ ቦ ለውጤት ያበቃ ባህሪ ለሌላም ሊያበቃ የሚችል ሲሆን አንድ ቦታ ላይ ተፈትሾ ያልሰራ ባህሪ ደግሞ በሌላ ቦታ ላይም ሊራ አይችልም፡፡ ሆኖም ለብዙ ተቋማት ውድቀት ትልቁ ምክንያት ያ ተቋም የሚፈልገውን ልዩ የአመራር ባህሪ ካለመኖር ወይም ደግሞ ካለማዳበር የሚመነጭ ነው የሚሆነው፡፡ ለዚያም ነው አንዳንዴ በአመራር ብቃታቸው ሌላ ቦታ ውጤታማ ሆነው በሌላ ድርጅት ላይ ሲቀጠሩ ድርጅቱን ሊጥሉት የሚችሉት፡፡ ይህም ማለት ባህሪ በየጊዜው የሚዳብር፣ እንደምንመራው ተቋም ባህሪም በአዲስ መልክ የሚሻሻልና ውጤትን የሚወስን አንዱ የመሪዎች ወሳኝ ገፅታ መሆኑን ነው፡፡
2. A Attitude… አመለካከት
“If your actions inspire others to dream more, learn more, do more and become more, you are a leader” John Quincy Adams
ይህ የመሪዎች ሌላኛው ውጤት ቀያሪ መገለጫቸው ነው፡፡ የመሪዎች ገንቢ አመለካት ለገንቢ ውጤት የሚያበቃ ኃይል አለው፡፡ አንድ መሪ የድርጅቱን ራዕይ የራሱ ራዕይ አድርጎ ከመነሳት ይጀምራል፡፡ አንዳንድ አመራሮች በአንድ ተቋም ላይ ለመሪነት ሲመረጡ ወይም ደግሞ ሲሾሙ የድርጅቱን ራዕይ ላያውቁት ወይም ደግሞ ላያምኑበት ከቻሉ ግለሰቡና ተቋሙ አልተዋወቁምና ከዚህ መሰል አመራር ውጤት መጠበቅ ማለት ከጠራ ሰማይ ላይ ዝናም ይጥላል ብሎ ጥላ እንደመያዝ ነው የሚቆጠረው፡፡ እንዲሁም የትኛውም የንግድ ተቋም ስራውን የሚገዳደሩት ተወዳዳሪ ተቋማት አሉ፡፡ የንግድ ድርጅትን ብንወስድ ከእነሱ ካልተሻለ ሊጥሉት የሚችሉ ተወዳዳሪዎ አሉት፡፡ በንግድ ውስጥ ያለው አማራጭ፣ ወይም መምራት አልያም መውጣት ነው፡፡ ከፊት መሪዎች ውስጥ አንዱ መሆን መቻል አለበት፡፡ የእግርኳስ ክለብንም ብንወስድ እንዲሁ ነው፡፡ የፖለቲካ ፓርቲም ተፎካካሪዎች አሉት፡፡
በመሆኑም የትኛውም ተቋም በአሸናፊነት መንፈስ የተገነባ አመራር ያስፈልገዋል፡፡ ተቋሙ ከሌሎች ተሽሎ የሚገኝ ተቋም እንደሆነና እሱም ያንን በተግባር እውን ማድረግ እንደሚችል የሚያምን፣ ቁርጠኝነቱ ያለው፣ አመራር ያስፈልጋል፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ራሱንና ተቋሙን አሳንሶ የሚመለከት አመራር እኩል ውጤት ሊያመጣ አይችልም፡፡
እንዲሁም የድርጅቱ ውጤት የእኔ ውጤት ነው፤ የድርጅቱ ውድቀት የእኔ ውድቀት ነው ብሎ የሚያምን አመራርም ያስፈልጋል፡፡ የትም ቦታ አንድ መሪ ስራውን ቀይሮ ቢወጣ ለሌላ አመራርነት ሊታጭ የሚችለው ከአሁን ቀደም በመሪነት ደረጃ ያመጣቸው ውጤቶች ታይተው ነው፡፡ የመሪው ህልውና በቀጥታ ከተቋሙ ህልውና ጋር ይያያዛል፡፡ ዛሬ ላይ ለውጤት ያበቃ ባህሪ ነገ ሌላ ቦታ ላይ ይኸው ባህሪ አብሮት ይዘልቃል፡፡ ተቃራኒውም እንዲሁ ነው፡፡ በመሆኑም በአመራርነት ደረጃ ላይ እስከተቀመጠ ድረስ የተቋሙ ውጤት የእኔ ውጤት ውድቀቱም የእኔ ውድቀት ነው ብሎ ማመን መቻል ይኖርበታል፡፡ ይህ እንደ መሪ የሚያስፈልግና ለውጤት የሚያበቃ አመለካከት ነው፡፡

3. S-skill…ችሎታ
“A man who wants to lead the orchestra must turn his back on the crowd!” Mad Lucado
መሪነት ራሱን የቻለ ችሎታም ነው፡፡ ከሚመሯቸው በላይ የላቀ ችሎታን ይጠይቃልና አውቶብስ መንዳት ራሱን የቻለ ችሎታ ነው፡፡ ተቋምን መሾፈርም እንደዚሁ፡፡ የትኛውን ማርሽ በየትኛው ጊዜ ላይ ወስኖ መጠቀም እንዳለበት መረዳት የሚችል፤ የትኛውን ቁልፍ መንካት እንዳለበትና እንደሌለበት ማወቅ የሚችል፤ አቅጣጫን የመረዳት ችሎታ፣ የመኪናውን ባህሪ የመረዳትና ማስተካከል የሚችል ችሎታ ያስፈልገዋል፡፡ አንድ የተቋም አመራርም በተግባር የተፈተሸ ልዩ ልዩ ችሎታዎች ያስፈልጉታል፡፡ ገንዘብ የማስተዳደር ችሎታ፣ ሰው አስተዳድሮ የማሰራት ችሎታ፣ ስሜቱን የመቆጣጠር ችሎታ፣ ውጤታማ ኢንቨስትመንት የማድረግ ችሎታ፣ ተናግሮ የማሳመን ችሎታ፣ የማቀድ ችሎታ፣ የወደፊቱን የመተንበይ ችሎታ፣ እያለ ይቀጥላል፡፡ አንድ አመራር ጥሩ ገንቢ አመለካከት ቢኖረው እንኳን ትክክለኛ ችሎታ በሌለበት ሁኔታ ያለትክክለኛ ትግበራ የሚጠበቀውን ትክክለኛ ውጤት ለማምጣት ያስቸግረዋል፡፡
4. K- Knowledge…
“It the blind lead the blind, both shall fall in the ditch”… Jesus Christ
በእርግጥ ችሎታ የሚዳብረው ከማወቅ ነው፡፡ ለአመራርነት የሚያበቁ ችሎታዎችን ለማዳበር በቅድሚያ ስለችሎታዎቹ መሰረታዊ እውቀት ሊኖረው ይገባል፡፡ ሁሉም አይነት እውቀት አይደለም፣ ለትክክለኛ ቦታ የሚሆን ትክክለኛ እውቀት እንጂ፡፡ ይህ ብቻ አይደለም፣ ስለሚመራው ተቋምም ውስጣዊና ውጫዊ ሁኔታዎችን ሊያውቅ ይገባል፡፡ እንዲሁም የሚመራው አንድን የንግድ ተቋም ከሆነ ስለንግድ አሰራር መሰረታዊ እውቀት ያስፈልገዋል፡፡ ብዙውን ጊዜ በአገራችን የድርጅቱ ባለቤት ስለሆኑ ብቻ እንጂ መሰረታዊ የንግድ ‹‹ሀሁ›› እውቀት ኖሯቸው ድርጅታቸውን የሚመሩ ሰዎች ጥቂት ናቸው፡፡
አንድ ሰው የሚመራው የእግርኳስ ክለብን ከሆነ ደግሞ ስለ እግርኳስ መሰረታዊ እውቀትን ሊጨብጥ ይገባል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲም ከሆነም ስለፖለቲካና አገራዊ አመራር ትክክለኛ እውቀት ያስፈልገዋል፡፡ ምክንያቱም እውቀቱ ችሎታውን ይወስናል፤ ችሎታውን ተግባሩን፡፡ ተግባሩ ደግሞ ባህሪውን ይቀርፃል፡፡ በመጨረሻም የግለሰቡንና የተቋሙን ውጤት፡፡
ለምሳሌ በአገራችን ያሉ መካከለኛና ከፍተኛ የሚባሉ ኢንተርፕራይዞች በቀጥታ ለመመራት ያለባቸው በቢዝነስ ሁለተኛ ዲግሪ ባላቸው ባለሙያዎች ሲሆን ብዙዎቹን ስንመለከት ግን ይህን ሚዛን አያልፉም፡፡ ለዚያም ነው የሚመሯቸው ተቋሞች ወደ ላይና ወደ ታች ሲሉ የምናያቸው፡፡ በፓርቲም ደረጃ እንዲሁ በፖለቲካል ሳይንስ በቂ ግንዛቤ ያላቸውን አመራሮች ይጠይቃል፡፡ አለበለዚያ አላዋቂ ሳሚ እንዳይሆን ራሳችንን መፈተሽ ይገባል፡፡ ለትክክለኛ ተቋምና ለትክክለኛ የአመራር ቦታ ብቁ የሚያደርግ ትክክለኛ እውቀት!!
5. E- Experience…  ልምድ
“Leadership and (experience) are indispensable to each other”… John f. Kennedy
ከላይ ያሉት የአመራር ችሎታዎች የሚዳብሩት በልምድ እና በልምምድ ውስጥ ነው፡፡ እንዲሁም የአመራርነት ባህሪ በራሱ የልምድ ውጤት ነው፡፡ ከአሁን ቀደም አንድ ሰው ያዳበረው ልምድ ውጤት የማያመጣ ወይም የውድቀት ከሆነ ባህሪውም ይሄንኑ ነው፡፡ በእርግጥ የአመራር ችሎታዎቹም ቢሆኑ ውድቀትን የሚያላብሱ ናቸው የሚሆኑት፡፡ በሥራ ማስታወቂያዎች ላይ ‹‹በዘርፉ ይህን ያህል የሥራ ልምድ›› የሚባለውም ለዚያ ነው፡፡ የአንድን አመራር ልምድ በቀላሉ ለመረዳት ‹‹ከአሁን ቀደም ምን ያህል ድርጅቶች አቋቁመህ ወይም መርተህ ለውጤት አብቅተሃል?›› የሚለው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡ አንዳንዱ ረጅም ዓመት የመምራት ልምድ ኖሮት ሊሆን ይችላል፡፡ ዋናው ነገር በቦታው ላይ መቆየቱ አይደለም፡፡ ድርጅቱን ከየት አንስቶ የት አደረሰው? የገጠሙትስ ተግዳሮቶች ምን ነበሩ? እንዴትስ በመፍታት ተቋሙን ለውጤት አበቃው? ነው ጨዋታው፡፡ አመራርነት ስልጣን አይደለም ውጤት እንጂ፡፡ ማዕረግ አይደለም፡፡ አፈፃፀም እንጂ ረጅም ዓመታት በመምራት መቆየትም አይደለም ረጅም የሚያስከነዳ ውጤትን ማስጨበጡ ላይ ነው ቁም ነገሩ፡፡
6. T- Talent… ልዩ ብቃት
“Your are your master, only you have the master key to pen the inner locks!”
…Leonardo Davienchi
ይህ የአመራርነት የመጨረሻው ማስተሪ ይሉታል ባለሙያዎች፡፡ መሰጠት እንደማለት ነው፡፡ ታለንት በተፈጥሮ የተሰጠን ሊሆን ይችላል፡፡ በትምህርትና ልምምድም ወደ ማስተርነት የተቀየረም ሊሆን ይችላል፡፡ ከላይ ያሉት ውጤት ተኮር እውቀቶች፣ ውጤት ተኮር ችሎታዎች፣ ውጤት ተኮር አመለካከቶች፣ ውጤት ተኮር ልምዶች በየጊዜው በዳበሩ ቁጥር ግለሰቡ ለዚያ ቦታ የሚኖረው ልቀት ያለው አመራር (Leadership excellence) ወደ ፍፁም ብቃት ይሸጋገራል፡፡ ውጤታማ አመራርነት ለግለሰቡ ቋንቋው፣ ተግባሩ፣ መንፈሱ፣ መሆን ሲጀምር ሊደርሺፕ በራሱ ታለንት ወደ መሆን ተሸጋገረ እንለዋለን፡፡
ለዚህ መሰሉ ሰው ውጤታማ አመራርነትን አውቆት ወይም አስቦበት ሳይሆን ሳያውቀው ሁሉ የሚተገብረው ነው የሚሆነው (autopilot)፡፡ የሊደርሽፕ ማስተሪ ማለት ይህ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በአመዛኙ የምናየው የትምህርት ማስተርስ እንጂ ውጤትና ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ማስተሪ አይደለም፡፡ ይህ ምናልባት የትምህርት ተቋሞቻችን አንዱ ክፍተት ሊሆን ይችላል፡፡
ለምሳሌ እኔ ባለፍኩበት የህክምና ሳይንስ ተቋም ማለትም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንደ ህክምና ሳይንስ አመለካከታችን በሔታክራተሳዊ ኤቲክስ፣ እውቀቱ ረጅም ዓመታት የሚፈጅ፣ ከመጀመሪያው ዓመት ጀምሮ በፍፁም ተግባር ላይ የተንተራሰ፣ ለሶስት ዓመታት ያህል ከሲኒየር ሐኪሞች ስር በመሆን እንደ ሐኪም ህሙማንን በመመርመርና በማገዝ፣ በተለያዩ ሆስፒታሎች በመዘዋወር ውስጥ ተሞክሮ የተገነባበት በመሆኑ አንድ የህክምና ዶክተር ከተመረቀ ጀምሮ በየትኛውም ቦታ ላይ የሚገጥሙትን የስራ ላይ ተግዳሮቶች መወጣት ይችላል፡፡ ድንገተኛ ቀዶ ህክምና አስፈልጓቸው በገጠሩ በቂ መብራት በሌለበት ሁኔታ ውስጥ እንኳን ቀዶጥገና አድርገው ህይወት ያተረፉ፣ እንደዚሁም በቀዶ ህክምና ያዋለዱ ተመራቂ ጓደኞች ነበሩኝ፡፡ በመሆኑም ሁሉም የትምህርት ተቋማት ከላይ ያሉትን የአመራር ገጽታዎችን በተሞላ መልኩ የገነቡ ተተኪ ወጣቶችን ለማፍራት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለይ የህክምና ሳይንስ ኮሌጆችን ተሞክሮ ቢወስዱ የሚል እምነት አለኝ፡፡
እንዲሁም በዓለማችን ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አንዱ ከሆነው የአሜሪካው ስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ከሚመረቁ አምስት ሰዎች ውስጥ አንዱ በአምስት ዓመት ውስጥ ውጤታማ የድርጅት ባለቤት ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ደግሞ አለማቀፍ ኩባንያዎች ውስጥ የአንዱ አገር ዲቪዥን የበላይ አመራር ሆኖ የመቀጠር እድል አለው፡፡ ይህ የሚያሳየው ዩኒቨርሲቲው የሚያወጣቸው ተማሪዎች የ‹‹BASKET›› ፅንሰ ሃሳብን በተላበሰ መልኩ ስለሚያስተምሯቸው ነው፡፡ በነገራችን ላይ የስመ ገናናው ኢሲኤክክስ መስራች ዶ/ር እሌኒ ገ/መድህን የዚህ ዩኒቨርሲቲ ውጤት ናት፡፡ ዩኒቨርሲቲ በንግድ ሳይንስ ካስተማራቸው ውስጥ በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ 30 በህይወት ያሉ ቢሊየነር ነጋዴዎችን ማፍራት የቻለው ከዚህ አንፃር ነው፡፡ እንግዲህ ቢሊየነሮቹ ይህን ያል ከሆኑ መልቲ ሚሊየነሮቹ ምን ያህል ይሆኑ? ሚሊየነሮቹስ? እጅግ ብዙ፣ ይህን በእኛ ሀገር ብንፈትሽ ስንቶቹ የንግድ ሳይንስ ተማሪዎች የት ደርሰዋል? ብለን ማንሳትና ማጥናትም አለብን፡፡
እናም በየትኛውም ተቋማት ውስጥ ለምንቀጥራቸው አመራሮች እንደመመልመያ መስፈርትም ሆነ መገምገሚያነት እንዲሁም ተተኪ አመራሮችን ወደ ላይ ለማምጣት የ‹‹B ASKET›› መርህን መከተል እንችላለን፡፡ በምንመራው ተቋም ውስጥም ልንጠቀምበት እንችላለን፡፡ እንዲሁም በዚህ መርህ ተተኪ አመራሮችን በኮችንግ፣ በስልጠና እንዲሁም ከበላይ ካሉ አመራሮች ስር በመሆን እንዲሰሩ በማድረግ ማብቃት እንችላለን፡፡ በተላዩ የድርጅቱ ክፍሎችና ቅርንጫፎች ውስጥ በማዟዟር ልዩ ልዩ እውቀትን፣ ልምድንና ችሎታን እንዲያዳብሩ ካደረግን በኋላ ወደ ላይ ማምጣት እንችላለን፡፡
መንፈሳችን ስለወደዳቸው፣ ደስ ስላለን ወይም ስለመሰለን የምነቀጥራቸው ወይም ደግሞ የምንተካው ሰዎች መኖር የለበትም፡፡ ደስ ስላለን ብቻ መኪናችን እንዲነዳልን ቁልፍ ሰጥተን በመኪናው ውስጥ ተሳፍረን የምንሄድ ስንቶቻችን ነን? አናደርገውም፡፡ ተቋምም እንዲሁ ነው፡፡

ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች የነጻነት አጋሮች |የሳዲቅ አህመድ ልዩ ፕሮግራም

$
0
0


በህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ የሚመራዉ መንግስት ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች ለማጋጨት ያደረገዉ ሙከራ ዉጤት አላመጣለትም። ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች በአገርም ዉስጥም ይሁን ባህርማዶ የነጻነት አጋር በመሆን ብሔራዊ ጭቆናን እየተጋፈጡ ይገኛል።ለዘመናት ተከባብረዉና ተዋደዉ የሚኖሩትን ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች ከህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ ነጻ ለመሆን የሚያደርጉትን የወል ትግል በመቃኘት ሳዲቅ አህመድ ልዩ ፕሮግራም አዘጋጅቷል።


Sadik Ahemed Journalist

ዶ/ር አብደላህ ሀሰን አል ቱራቢ ማን ናቸው?

$
0
0

turabu

… በያዝነው ሳምንት በ84 ዓመታቸው በዋና ከተማዋ ካርቱም መሞታቸው የተነገረው ዶር አብደላህ ሀሰን አልቱራቢ በልብ ህመም ሳቢያ ከዚህ ዓለም እስከተለዩባት ቀን በሱዳን የፖለቲካ ህይዎት ቁልፍ ቦታዎችን ይዘው ያንቀሳቀሱ ስመ ገናና ነበሩ። አገሪቱ በእስልምናው የሸሪአ ሕግ እንድትመራ የመሰረት ድንጋዩን አሳምረው የጣሉ ፖለቲከኛነታቸው ቱራቢ በሚወዷቸው ዘንድ ለሙስሊሙ ብሩህ ህይወት ቅን አሳቢ እየተባሉ ይወደሳሉ። ቱራቢ በአገራቸው ፖለቲካ አልፎ ለጎረቤት ሀገራት ተጽእኖ ፈጣሪ በነበሩባቸው ጊዜያት አገሬው ጠበቅ ባለው የእስልምና አስተምሮትና አካሄድን እንዲከተል እና የሸሪዓ ሕግ እንዲተገበር የማዕዘን ድንጋይ መጣላቸው ይነገራል። በተለይም ዓለም በአሸባሪነት ከፈረጃቸው ከሸህ ኦሳማ ቢንላደን ጋር የነበራቸው ግንኙንት ሲጠቀስ ይህም የኦሳማ ቢላዲን ባላንጣ የሆኑት ምዕራባውያን ቱራቢን በአይነ ቁራኛ እንዲያዩዋቸው ምክንያት መሆኑ ይጠቀሳል። በአንጻሩ አክራሪነትን በሱዳን ያስፋፉ ፖለቲከኛ እንደሆኑ የሚወነጅሏቸው ሱዳናውያን የፖለቲካ ተንታኞች ፖለቲካውን ከሃይማኖት ደባልቀው ለተደጋጋሚ ግጭት አገራቸውን ዳርገዋል ሲሉ ይነቅፏቸዋል።

ቱራቢ ከፕሬዚደንት አልበሽር ጋር መጣላታቸውን ተከትሎም የሱዳን ፖለቲካ በከፍተኛ ሁኔታ ለዓመታት እንዳይረጋ ቆስቋሽና ዋነኛው ችግር ፈጣሪ እንደነበሩ የሚናገሩት የአገሪቱ የፖለቲካ ተንታኞች ሱዳን እንዳትረጋ ቱራቢ እጃቸው ረዥም እንደነበር ይናገራሉ። በ1991 ከቀድሞ ወዳጃቸው ከፕሬዚደንት አልበሽር ጋር በወንበርና ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች የተቃቃሩት አልቱራቢ ከ1999–2016 ‹‹Popular Congress Party›› የተባለ የተቃዋሚ ፓርቲ መስርተው በመምራት ላይ ነበሩ። ዳሩ ግን በተዋቃዋሚ ፖርቲ መሪነት ባሳለፉአቸው ሁለት አስርት ዓመታት ከአልበሽር ጋር በፈጠሩት ተደጋጋሚ ፍጥጫ በተደጋጋሚ ለእስር ተዳርገው ያውቃሉ። ዶር ቱራቢ እንግሊዝኛ፣ ፈረንሳይኛና ጀርመንኛ አቀላጥፈው የሚናገሩ አንደበተ ርቱዕ ተናጋሪ፣ ጸሐፊና መጽሐፍ የማንበብ ልምዳቸው አስገራሚ የሆኑ የሱዳን ፖለቲከኛና የሃይማኖት ልሂቅ ነበሩ።

ሙሉ ዘገባየን ዛሬ ሐገር ቤት በምትወጣው የቀለም ቀብድ ጋዜጣ ያገኙታል !

ነቢዩ ሲራክ
የካቲት 29 ቀን 2008 ዓም

አገር በሕወሓት ቀጥተኛ አገዛዝ ስር

$
0
0

hailemariam and samora
ኦሮሚያ በወታደራዊ አገዛዝ ስር የሚለውን ቀድመው  በወታደራዊ አገዛዝ ሰር የገቡትን የኦጋዴን የጋንቤላና የአፍር ክልልችን ጨምሮ በአሁኑ  ጊዜ ኢትዬጵያ  በወታደራዊ አገዛዝ ስር ወድቃለች ማለት ይቻላል።  ስላሉት ነው እንጂ ጉዳዩን ወታደራዊ የሚባል ነገር  የሚገልፀው አይደለም።  ወታደራዊ አመራሮቹ በሙሉ ከአንድ ዘርና ድርጅት መሆናቸውን የምናውቀው ነው።  ህዋዋት ተቆጣጠረው መቼም እንዲሉ አይጠበቅም።  ለሁሌው ህዋዋት የሚታዘዙለትንና የተመቹትን ከሌሎች ብሔረሰቦች ይዞ በፍፁም የበላይነት ገዥ ነው። ይህም ሆኖ እንኳ እስከጭራሹ “ትግሬ” ያልሆኑ መኖራቸው ሰላም ሰጥቷቸው አያውቅም። ለዚህ ቶሽ ባለና አደጋ በሸተተቻው ቁጥር ተሯርጠው ስልጣኑን ይቀበሏቸዋል።  ሰብስቦ ማሰር የተለመደ ነው። በአንዴ እስከ ሶስት መቶ የሚደርሱ ተሰብስበው የታሰሩበት ጊዜ አለ። የተገደሉም እንዲሁ። ለተጣመሯቸው ወከልነው ያሉትን ህዘብ ባደባባይ ማዋረድና  ተቃርኖ መቆም ያገልግሎታቸው አንዱ ክፍል ግዴታም ነው። ወገኖቻቸውን ማስገደል ማሳሳር ማስደብደብም ቢያማቸውም እንዲሁ። ሌላ ቀርቶ አገልጋዬች የነበሩ ሸሽተው ሂወታቸውን አትርፈው  ነፃነታቸው ግን አሁንም በህዋዋት እጅ ያለ ብዙ መሆናቸውን እየሰማን ነው። በመሳቀቅ የሚኖሩትን እግዚአብሔር ይቁጠራቸው። ያው ሁሉም ናቸው። ለምን? የሚለው ቀላል መልስ የለውም። ለሚታገለው ይህ መሆኑ  ቢያሳዝንም ይጠቅማል።

በወታደራዊ አመራር ስር የሚለው እንደተለመደው  ያሉትን አስተዳደራዊ መዋቅሮች በሙሉ የናቀና ህልውናቸውን አጠራጣሪ አድርጓል። እያጫጫቸውም እየሄደ ነው። ። ጠቅላይ ሚንስትር ምናምነቴ፤ ፓርላማ፤ ምክር ቤት፤ ፌደራሊዝም፤  የከልል መንግስታት፤ሚኒስቴር ማስራቤቶቹን ሁሉ ጨምሮ። ያም ሆኖ መፈንቅለ ወታደር ግን አይደለም። መፈንቅለ ወታደር የሚሆነው ህዋዋቶችን በልተው የሌላ ብሄር የበታች ሹመኞች ቢመጡ ነበር።  ለዚህ የተመቻቸ ሁኔታ እየተፈጠረ ግን ይመስላል።  የሚያስፈራ ደግሞ አይደለም። የለውጡ አጋዥ አካል እንጂ ወታደራዊ መንግስት የመሆን እድላቸው ለነሱም የሞተ ነው። ዘመኑም የመሀበረሰባዊ እድገታችንም ይህን አይፈቅድም። ሂደቱ ያለየለትና ግልፅ ብሎ የሚታይ አይደለም ለጊዜው።  ምሁራኖቻቸው ግን እራሳቸውን በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በሚመስል ነገር እንደእስስት  ቀይሮ ትንሽ ማሻሻያ አድርጎ መምጣቱን እንደ አንድ ማምለጫ ብልሀት አድርገው መምከር ከጀመሩ ከራርመዋል።

የቸገረው ነው ነገሩ። ጠቅለል አድርጎ ፍፃሜያቸውን ሊያደርጉ  ወደ ሚችሉና አቅሙና ፍላጎቱ ወዳላቸው ነው የተጠጉት። ፖለቲካዊ ውጥንቅጡን ያስተላለፉት ማለት ይቻላል። ጥሩነቱ ከአጋር ድርጅቶች በላይ  መሳርያ የያዘው ክፍል የህዋዋት የበላይነት እንዲያከትም የሚፈልግበት ምክንያቶች የበዛ ነው። ምሬቱና የለውጥ ፍላጎቱ  አሁን እየተጨፈጨፈ ካለው የኦሮሞ ህዝብም በላይ ነው ቢባል ማገነን አይሆንም። በዛ ላይ በሂደቱ  ወደመጡበት ህዘብ ጋር ነው የሚያደባልቃቸው። ስለዚህ እነሱም ያምፃሉ። ለዚህ  የዚህች አገር ችግሮች ህዋዋቶች መሆናቸውን ማወቃቸው ብቻ አይደለም። ዋናው ቁም ነገር ችግር ፈጣሪዎቹ ተለይተው ግልፅ ብለው ትንሽ ስብስቦች ሆነው ከመቼውም ጊዜ በላይ  አንሰው መታየታቸው ነው።  ከህዘብና ከነሱ ለመምረጥ ቀላል ሆኗል። በተጨማሪም የስርአቱን መበስበስና መበሳበስ ከውጪ ካለነው በላይ አብረዋቸው በቅርብ ላሉት ግልፅ ብሎ የሚያዩት ነው።  መሳርያ በጁ ያለውን በተመለከተ ለኛም ለነሱም አብሪ የሆኑ ለጥቃቅን ነገሮች ጥቃቅን የሆኑ አመፆችን በበቂ የማናየው የማየምች ስለሆነና አደጋው ስለሚሰላ ነው። እንደ ኦፒዲዬ ማለት ነው። ከውስጥ ስትሆን ጊዜና ሁኔታዎችን ታሰላለህ። ጠቅለል ባለ መልክ መሳርያ በጁ ባለውና በአንባገነን ገዥዎች መሀል ያለው ጠቅላላ ግንኙነት እዚህ ደረጃ ሲደርስና ይህን አይነት መልክ ሲይዝ የህዝብ አልገዛም ባይነት እየጠነከረና እየሰፋ ሲሄድ የሚሆነው  አንዴ በትልቁ ይፈነዳል። ያኔ ከቅርብ አለቆች በመጀመር በሚያስጎመጉም ሁኔታ በአንድ ቀን ውስጥ ግልብጥብጡ ይወጣል። መረሳት የሌለበት ያው ይገላሉ፤ ያስራሉ.. ምን አዲስ ነገር አለው እያለ ሊገለፅ በማይቻል ቁርጠኛነትና ወኔ የሚታገል አዲስ ትውልድ ስርአቱ ፈጥሯል። ባለመሳርያው ከዚሁ ትውልድ  ውስጥ ነው። መገደለን የማይፈራ ትውልድ ገድሎ ነፃነቱን ማወጁ የማይቀር ነው።

በአጠቃላይ ወደመጡበት የሚለውን ትንቢት እየሰሩት ነው ማለት ይቻላል። ከዚህ በላይ ማለቱ  ጉዳት አለው። መንገዱችሁን ጨርቅ ያድርግላችሁ ብለን እንዝጋው። ወናው ነገር እያጋመ ላለው ህዛበዊ አልገዛም ባይነት ይህ ውሳኔ ለጊዜውም ቢሆን አሉታዊ ተፅኖ አለው ወይ? የሚለው ነው። “ጦርነት ከኤርትራ ጋር”። “ችግሩ የመልካም አስተዳደር ነው”። “ተገንጣዬች ናቸው”። “በወታደራዊ አመራር ስር”  ፖለቲካ ላይ  የጅምላ ዘግናኝ ጭፍጨፋ በማድረግ አመፁን ልናዳፍነው እንችላለን እቅዳቸው ነው። እነ ልደቱ ሁሉ አስተዋጿቸውን ተጠይቀዋል። በወታደራዊ አመራር ስር የሚለው ለጊዜው በመሬት ላይ የሚለውጠው ምንም ነገር የለም። አስፈራሪነቱን እንጂ እነሱም ይህንን ያውቁታል። ሲጀምር የኦሮሞ ህዘብ  ጨፌን ሊቃወም አደባባይ አልወጣም። የዘረፈውም የጨፈጨፈውም ኦፒዲዬ አይደለም። ኦፒዲዬዎች ግን ኦሮሞዎች ናቸው። በአጠቃላይ ህዋዋቶች የሚያጡት እንጂ በፊት ያልንበረ አሁን የሚያገኙት አዲስ ጉልበት የለም። ህዝቡ ይህንን አሳምሮ ስላወቀ አልገዛም ባይነቱን አበርትቶ ቀጥሏል። እንቢታው እየሰፋ አገራዊ መልክ እየያዘ ነው። ሌላው በቀጣይ የሚታይ ይሆናል። አንድ ጊዜ ላይ “መግደልም ይቸግራል” ብሎ ነበር ዶ/ር መራራ።

መሪን በሚመለከት።
በአደዋ ጦርነት መሪን ማጣት ወታደሩን እንደሚፈታው ከፄ ዮሀንስ አሟሟትና ሽንፈት ትምህርት  መወሰዱንና ተገቢው ጥንቃቄ መደረጉን  “አፄሚኒልክ ጦርነቱ ላይ ከፊት ለፊት አልነበሩም” ለሚል ትችት የተሰጠ መልስ ላይ ቆየት ቢልም አንብቤያለው። ይህን ያነሳሁት “መሪ ከፍትለፊት መሆን አለበት”። “መሪ የግድ አገር ውስጥ መሆን አለበት” ስለሚመሳሰሉ ነው። ክፍት ባይኖራቸውም ትክክል ቢመስሉም ቅሉ ዶግማ እየሆነ ትግሉን እየጎዳ ግን ነው።  ይህ ህዝባዊ እንቢታ ከተነሳ እንኳ ብዙዎች አስረገጠው ተናግረውበት አድምጠናል። ፅፈውበት አንብበናል። ሀሳቡ ካንጀት  የታመነበት ስለሆነ መሪ ሆኖ ወጥቶ ለመምራትና አቅጣጫ ላማስያዝ አይደለም ከውጭ ሆኖ ቃል አቀባይ መሆን እንኳ ችግር እየሆነ ነው። ጊዜው ትግል የሚገባቸው ብዙዎች አንድ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው ከፊትለፊታቸው ጥቁር ሰሌዳ ለጥፈው። ትልቅ ካርታ ሰቅለው። ቾክና እስቢል ባለበት፤ ስልክ አሁንም አሁንም በሚጮህበት ብዙ ወረቀቶች ጠረቤዛ ላይ ተደርድረው ፀጉር ሲነጩ ማደርን በፈረቃ ሁሉ ቀንና ሌሊት የሚሰሩበትን ሁኔታ ግድ የሚል ነው። አገር ውስጥ ይህን ማድረገ አይቻልም። ስለዚህ መስራት የለበትም ወይ?። እንደጎደለ በደንብ ይታያል። መራራ በሆነ መሰዋትነት ውስጥ መሬት ላይ የሚሰሩና እያስተባበሩ ያሉ ብዙ መሪዎች አሉ። ጉድለታቸውንና በነሱ ያልተቻላቸው በሚችሉ ሊሰራ ግን ይገባል። እየጠበቁም ነው። መሰዋትነቱን መና እንዳናስቀረው አንጃጃል።

ትግሉን በሚመለከት።

የኦሮሞ ህዘብ አልገዛም ባይነቱን ቀጥሏል። እየሰፋና ቀስ እያሉ ሌሎችም እየተቀላቀሉበት አገራዊ መልክም እየያዘ ነው። የህዋዋት እስትራተጂም ሆነ የህዘብን ትግል ለማንቋሸሽ የሚሯሯጡ ክፍሎችና ትግል አረጋጊዎች መባትል ሊገታው አልቻለም። ወያኔ ከመደንዘዝ ውስጥ ወጥቶ አንዳንድ ነገሮችን ሲሞክር እንኳ ታቃዋሚዎች ግን እንደደነዘዙ ነው። በእንቅልፍ ልብ ውስጥ ሆነው እንቢታው ሲጀመርና ግድያ ሲከተል የአቋም መግለጫ ነው የሚባለው ነገር ጫጭሩና ተመልሰው ተኙ። አልገዛም ባይነቱም ጭፍጨፋወም አራት ወር ሊሞላው ነው። እንቅልፍ ላይ ባይሆኑ ሌላ ማድረግ ባይችሉ ጭፍጨፋወን እንኳ እንዲሰማ አድርገው ደጋግመው ማውገዝ በቻሉ ነበር። ካንጀት ቢሆን ከህዘብ ትግል ጎን የሚያቆማቸው ብዙ ሊያደርጓቸው የሚችሏቸው ነገሮች ደግሞ አሉ።

ኦሮሞዎች እየደረጉ ያሉትን ትግል ለመደገፍ የሚቀመጡ ብዙ ቅድመ ሁኔታዎች ይሰማሉ። ማድረጉ ክፋት የለውም። ብሔራዊ ጭቆና ይብቃ ብሎ መፈክር ይዞ መውጣት ይቻላል። አፍ ለማዘጋት ይጠቅም እንደው እንጂ ጠያቂዎቹን ግን መቼም ተባባሪም ትግሉን በመልካም እንዲያዩት አያደርግም። ዜጋው የጋራ የሆነው ጭቆና የተፈጠረ መልካም አጋጣሚን መጠቀም ካወቀበት ብቻ አብሮ ይታገላል አለቀ።  እያየን ያለነውም ይህንኑ ነው። ከዚህ ውጪ ያለው ቅድመ ሁኔታና የጠያቂ መዓት ለማለት ያህል ብቻ ነው። ጨው ለራስህ ስትል ጣፍጥ ነው ነገሩ። ይህንን የስልምና እምነት ተከታዬች ትግል ወቅት ታይቷል። በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ብዙ ጥረዋል። ያም ሆኖ ጥያቄው ተለጥቶ ግብፅ ውስጥ ለተገደሉ ክርሲቲያኖች ይቅርታን ካልጠየቁ የሚል ድረስ ሄዷል። ስለሌው ቅኝት መፃፍ ቀላል ነው። የራስን ቅኝት ማስተካከሉ ነው ከባዱ የሆነው። ያኔም ሆነ አሁን ይህን አይነቱ ሰበብ  የህዝብን ትግል ለማንቋሸሽ ሲባል የሚደረግ ነው። ስለዚህም በትልቁ የተሳሳተ ነው።

ስለቅኝት ካነሰው አይቀር ዘንድሮ ያደዋ ድል ልዩ የሆነ ትኩረት ተሰጥቶታል። ያከበርነው ግን አደዋን ሳይሆን አፄ ሚኒልክን ነበር። ይገባኛል መሪ ስለነበሩ ትልቅ ቦታ አላቸው። ያም ሆኖ ማንም የማይክደው የአደዋ ተጋድሎ ከሚኒሊክ በላይ ነው። የዜጎች ለነፃነት የተደረገ ታሪካዊ ተጋድሎ ነው። አንዳንዶች ቁስላቸው ላይ አመድ ደምድመው ነው አደዋ ላይ ደግሞ የተዋጉት። ከገባን ጀግንነት ይህ ነው። ያም ሆኖ አወንታዊ በሆነ መንገድ ተጠቅመንበት ቢሆን መልካም ነበር። ለርካሽ ፖለቲካ ፍጆታ ሲባል አሳፋሪ በሆነ ሁኔታ አፅማቸውን አውጥተን መንጋጋና መንጋጋቸውን ይዘን ስንሳደብባቸው ነው የከረምነው። አደዋን መቃወምና ሚኒልክን መቃወም ምን እንዳገናኘው በጭራሽ አልገባኝም። አፄ ሚንሊክ ለረጅም ጊዜ አገር መርተዋል። አሁን በሂወት የሉም። ይጠቅማል ብሎ ደረቱ ላይ ለጥፎ እንደሚሄደው ዘቅዝቆ የሚለብሳቸው ካለም መብቱ ነው። ያለበለዚያ አፄ ሀይለስላሴ ስለተሸነፉ ሁሉ መልካም ስራቸው ይንቋሸሽ። መንግስቱ የሱማሊያ ጦርነት ወቅት መሪ ስለነበር ምንም ክፉ ነገር ስለሱ አይነገር። የሚያስፈራኝ መለስ ዜናዊን መቃወም የህዳሴውን ግድብ መቃወም  እንዳይባል ነው። በዛ ላይ አያቶቻችን ያን ሁሉ መሰዋትነት ከፍለውበት አሁን ከአገር አገር የለን።  ከነፃነት ነፃነት የለን። ማክበራችን ካልቀረ አሳልፈን የሰጠነውን ለማስመለስ ቁርጠኛነትን የምናሳይበት ቢሆን አይሻልም ነበር ወይ።

ዳዊት ዳባ
Monday, March 07, 2016

በውቀቱ ሥዩምን ጸበል ሒድ ብየው እሽ ብሎኝ ነበር፤ በእግዚአብሔር አለማመን (Atheism) እና ፍልስፍና ምንድን ነው?

$
0
0

Beweketu Seyoun joke about African leaders summit [Very Funny]

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

March 7, 2016 – ትንታኔ
አንድ ማኅበረሰብ ዓይናማ ያወቁ የበቁ የነቁ የጠነቀቁ ልበ ብርሃን ሊቃውንት ያግኝ ይውጡለት እንጅ መላ እሴቶቹን በሙሉ ማለትም ወጉን፣ ባሕሉን፣ አስተሳሰቡን፣ ማንነቱን፣ ታሪኩን፣ ሃይማኖቱን ወዘተረፈ. እንዲፈተሽ፣ እንዲተች የግድ መፍቀድ ይኖርበታል፡፡ ካልሆነ ችግር አለ ማለት ነው፡፡ ለመፈተሽ ለመተቸት ካልፈቀደ እንዲታይ እንዲገለጥ የማይፈልገውና ቢታይ ቢገለጥ ቢተች የሚያፍርበት የሚሸማቀቅበት አንዳች ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ይሄ ከሆነ ደግሞ ዐይናቸውን የገለጡቱ የበራላቸው ሀገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነት አለባቸውና እነኝህ ምሁራን ዝም ማለት ስለማይችሉ ስለማይኖርባቸውም የማኅበረሰባቸውን ጠንቀኛ አስተሳሰቦች ለመንቀስ ለመቅረፍ በፈለጉ ጊዜ በልኂቃኑ አቀጣጣይነት ከማኅበረሰቡ ጋር ግጭት የሚፈጠር ይሆናል፡፡ በዚህ ዓይነት አጋጣሚዎች ከጥንት ጀምሮ በመላው ዓለም ልማዳዊና ባሕላዊ አስተሳሰብ ከተጫነው ማኅበረሰብ የወጡ ዓይናሞች ተወግረው እስከ መገደል በእሳት እስከ መቃጠል እስከ መሰቀል ድረስ ደርሰው እንዲጠፉ ተደርገዋል፡፡ የብዙዎቹ አስተሳሰብ ዓለም እየሠለጠነ ሲሔድ እውነት መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ ይሄም ሆኖ አሁንም ድረስ ብዙዎቻችን ፍልስፍናን የምንረዳበት መንገድ የተሳሳተ ነው፡፡

በዚህ ወቅት አስቀድሞም በነበረው ትውልድ ተማርኩ የሚሉ በርካታ ወገኖች ምሁርነትና ፈላስፋነት ማለት በእግዚአብሔር አለማመን፣ ሃይማኖትን መቃወም ማረካከስ፣ ማኅበረሰቡ ተቀብሎት ከሚኖረው እውነት፣ ሥነምግባር፣ ግብረግብ፣ የሞራል (የቅስም) እሴቶች ጋር መጋጨትን አለመቀበልን የመማራቸው ማረጋገጫ አድርገው ለማሳየት ይጠቀሙበት ነበር እየተጠቀሙበትም ይገኛሉ፡፡ በእግዚአብሔር ማመንንም ሞኝነት ቂልነት ለማስመሰል ጥረት ሲያደርጉ ይስተዋላሉ፡፡

በእግዚአብሔር አለማመን መብት ቢሆንም “እንዴት?” እና “ለምን?” ለሚሉት ጥያቄዎች ግን መልስ መስጠት አመክንዮአዊና ሞራላዊ (ቅስማዊ) ግዴታ መሆኑን፤ ለእነኝህ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ሳይችሉ በእግዚአብሔር አላምንም ማለት እጅግ የወረደ ማንነት ወይም ድንቁርና ስለመሆኑ ወይም ይሄ አመለካከታቸው ምን ያህል የተሳሳተና ያልበሰለ እንደሆነ በዚህ ጽሑፍ ላይ በስፋት እናያለን፡፡ ሁሉንም ዓይነት አንባቢ ሊገባው በሚችል መልኩ ግልጽ በሆነና በተብራራ መልኩ በመጻፉ ሁላችሁም ይገባቹሀል ብየ ተስፋ አደርጋለሁ መልካም ንባብ፡-

ፍልስፍና ማለት ምን ማለት ነው? ለዚህ ጥያቄ ባጭሩ መልስ ስንሰጥ፡- ፍልስፍና ማለት በእግዚአብሔር አለማመን ሃይማኖትን፣ መቃወም፣ ማረካከስ፤ ማኅበረሰቡ ተቀብሎት ከሚኖረው ባሕል፣ ወግ፣ ሥርዓት፣ እውነት፣ ሥነምግባር፣ ግብረገብ፣ የሞራል (የቅስም) እሴቶች ጋር አለመስማማት መቃወም ማለት ሳይሆን ያልታየን ያልተደረሰበትን እውነት መግለጥ ማሳየት ማለት ነው፡፡

እርግጥ ነው በዓለማችን ጥቂት የማይባሉ ፈላስፎች በእግዚአብሔር መኖር የማያምኑ አሉ፡፡ በእግዚአብሔር የማያምኑ እንዳሉ ሀሉ ደግሞ የሚያምኑም የሚያምኑ ሲባል በጣም የሚያምኑም አሉ፡፡ “የማያምኑቱ የእግዚአብሔርን አለመኖር ስለደረሱበትና እውነት ስለሆነ ነው ወይ የገለጡት የተናገሩት?” ካላቹህኝ አይደለም ነው መልሱ ዝርዝሩን ወደ ኋላ እናየዋለን፡፡

በእግዚአብሔር መኖር ከሚያምኑት ታዋቂና ታላላቅ ፈላስፎች ጥቂቶችን እንጥቀስ ካልን ካንት፣ ሔግል፣ ዲስካርትስ፣ ፊችት፣ ሌይብኒዝ፣ ሩሶው፣ ኪከርጋርድ፣ ማሪቴይን፣ ዊትገንስቲ፣ ዌይል የመሳሰሉት በእግዚአብሔር ላይ ጥልቅና ጥብቅ እምነት ያላቸው በመባል ይጠቀሳሉ፡፡

እንዲሁም ከአንጋፋ ሳይንቲስቶችም እንጥቀስ ከተባለ ቀደምቱና አንጋፋው የሃያኛው ምእት ዓመት መጣቂ (ሳይንቲስት) እ.ኤ.አ. (1879-1955) አልቨርት አንስታይንን በቅድሚያ እናገኛለን፡፡ እሱ እንዲያውም አንድ ተወዳጅ አባባልም አለው “Science without religion is lame, religion without science is blind.” “መጣቅ (ሳይንስ) ያለ ሃይማኖት ሽባ ነው፤ ሃይማኖት ያለ መጣቅ እውር ነው” በማለት የተናገረው አባባል ይጠቀስለታል፡፡

የተቀሩት ደግሞ እነ ማክስ ፕላንክን (1858-1947) ዊሊያም ቶምሰን  ከልቪንን (1824-1907)  ግሪጎር ሜንደልን (1822-1884) ሚካኤል ፋራዴይን (1791-1867) ሮበርት ቦይልን (1791-1867) ኢሳክ ኒውተንን (1642-1727) ብሌይዝ ፓስካልን (1623-1662) ሬን ዲስካርትስን (1596-1650) ጋሊሊዮ ጋሊሊን (1564-1642) ጆሐንስ ኬፕለርን (1571-1630) ሰር ፍራንሲስ ባኮንን (1561-1627) ኒኮላስ ኮፕርኒከስን (1473-1543) የመሳሰሉትን ታላላቅ ሳይንቲስቶችን መጥቀስ ይቻላል፡፡

በእውነቱ እኔ ሰው “በእግዚአብሔር አላምንም!” ሲለኝ ለእሌ የሚገባኝ ምን እንደሆነ ታውቃላቹህ? ዓይን አለኝ አላይበትም ጆሮ አለኝ አልሰማበትም ጭንቅላት አለኝ አላስብበትም ያለኝ ያህል ነው የሚሰማኝ፡፡ መመጻደቄ አይደለም ምን ማለቴ እንደሆነ ወደ ኋላ በደንብ ግልጽ ሆኖ ይገባቹሀል፡፡

አፍንጫችንን ተራራው ላይ አስነክተን በመጠጋት ዓይናችንን የቱንም ያህል ብንበለጥጥ ተራራው ላይ ያለችውን ጠጠር እንጅ ተራራውን አናየውም፡፡ በእግዚአብሔር መኖር አላምንም የሚሉ ሰዎች የተራራው መኖር እርግጥ ሆኖ እያለ የት ሆነው እንዴት ማየት እንዳለባቸው ካለማወቅ ተራራው የለም የሚሉ ናቸው፡፡ ማሰብ ማስተዋል ስለተሳናቸው እግዚአብሔር እንደተራራው የቅርብ እሩቅ ሆኖባቸው ነው እንጅ አእምሮ ልቡና ቢኖራቸው ማሰብ ማስተዋል ቢችሉ የእግዚአብሔርን መኖር እንደመረዳት እንደማወቅ የቀለለ ጥያቄ የለም! ስል ያለ አንዳች ማጋነን ነው፡፡

ሌላው ሁሉ ይቅርና በዙሪያቸው ያለውን ነገር ልብ ብለው ቢመለከቱ ሊመለስላቸው የሚችለውን ነገር ነው ሊያውቁት ያልቻሉት፡፡ እንበል ለምሳሌ ፍጥረታት ሁሉ ማለትም እንስሳት፣ አራዊት፣ አእዋፍ፣ ዓሣት ወዘተረፈ. ያስተማራቸው ያሳያቸው ሳይኖር እንዴት ኑሯቸውን እንደሚገፉ፣ ከሚገጥማቸው ፈተናና ጠላት እንዴት እራሳቸውን መጠበቅ መከላከል እንደሚችሉ አውቀው የኑሮ ሥርዓታቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ ማን አስቻላቸው? አስቀድሞስ ጠብቀውት የሚኖሩበትን ሥርዓት ማን አበጀላቸው? ጠብቀውት እንዲኖሩስ እንዴት አስቻላቸው? ፍየልን እባብ ከበላች በኋላ መርዙ እንዳይገላት ፈልጋ የምትበላትን ቅጠል የእባብ መርዝ ማርከሻ መድኃኒቱ ያች ቅጠል መሆኗን ማን ነገራት? ማን አስተማራት? እባብ መርዝ እንዳለውና ስትበላው እንደሚገላትስ ማን ነገራት? ሞታ የተነሣች ፍየል ፍየሎችን ሁሉ ሰብስባ ስለነገረቻቸው ነው? ወይስ ገበሬዎቹ እየነገሯቸው? ዶሮን የጣለቻቸው እንቁላሎች ጫጩት ሆነው እንዲፈለፈሉ ሙቀት መስጠት እንዳለባት አውቃ ለሃያ አንድ ቀናት መታቀፍ እንዳለባት አውቃ ያንን የምታደርገው ማን ነግሯት ነው? ገበሬዎቹ ይሆኑ?

ለእኛ ቅርብ የሆኑትን ምሳሌዎች ለመጥቀስ ያህል እንጅ ከእንስሳት ዓለም ስንት ድንቅና ግርም የሚሉ ትንግርቶችን ማንሣት በተቻለ ነበር፡፡ በናሽናል ጂኦግራፊ (በብሔራዊ መልክዓ ምድር) ድርጅት እየተዘጋቹ የሚቀርቡትን ቪዲዮዎችን (ትዕይንተ ኩነቶችን) ብታዩ ብዙ የምትረዱት ነገር ይኖራል፡፡

ፍጥረታቱ ሁሉ የነገራቸውና ያስተማራቸው ሳይኖር እነዚያን ኑሯቸውን የሚገፉባቸውን አስደናቂና አስገራሚ ዕውቀቶችን ያስተማራቸው ከሌለ ይሄንን ዕውቀት ይዘው እንዲፈጠሩ የሚያደርጋቸው ማን ነው? ተፈጥሯዊ ሕጋቸውን ጠብቀው ሳያፈርሱ የሚኖሩበትን ሥርዓት ማን ሠራላቸው? ያበጃጀው ያደራጀው የቀመረው ሳይኖር እራሱ በራሱ ጊዜ ተበጃጀ? ተቀመረ? ተሠራ? ተከወነ? ተወሰነ?

እስኪ ሰውነታቹህን ተመልከቱ ይህ አካላቹህ በተሳካ ሁኔታ እንዲያደርግ የሚጠበቅበትን እንቅስቃሴ ሁሉ እንዲያከናውን የአንጎል፣ የልብ፣ የሳንባ፣ የዓይን፣ የጆሮ ወዘተረፈ የተቀናጀ፣ የተሰናሰለ፣ የተናበበ ሥራን ይጠይቃል፡፡ እንዲህ እጅግ በረቀቀና እጅግ አስደናቂ በሆነ ሁኔታ የእያንዳንዳቸውን የሰውነት አካላት የሥራ ክንውናቸውን ለመረዳት ከአእምሮ በላይ በሆነ ችሎቻ አበጃጅቶ፤ የመጨረሻ ቀጭኗን የደም ስርና ጅማት ያለጥቅምና ያለአገልግሎት ሳያስቀምጥ እንዲያ እጅግ በጠወሳሰበ ሁኔታ እያንዳንዳቸውን ፈጥሮ እየተናበቡ ሥራቸውን እንዲሠሩ ቀምሮ ያደራጀው ማን ነው? እንዲህ ያለ የሰውነት አካል አስቦበት የሠራው፣ ያበጃጀው፣ የፈጠረው ሳይኖር እንዲሁ በአጋጣሚ ተፈጥሮ ይገኛል? ወይም ደግሞ እራሱን በራሱ ፈጠረ?

እንሒድ ወደ ላይ ወደ ሕዋው እንውጣ የሕዋ ተመራማሪዎች የአጠቃላዩን ዩኒቨርስ (ፍጥረተ ዓለም) ማለት የፕላኔቶቹን (የዐበይተ ከዋክብትን) ያሉበትን አቀማመጥ ዑደትና ተያይዘው ስላሉ ነገሮች ፍጹም (ፐርፌክት) በሆነ መንገድ በዓላማና በምክንያት እጅግ እጹብ ድንቅ በሆነ መንገድ ስለ መተለማቸው (ዲሳይን ስለ መደረጋቸው) ሲናገሩ አድንቀውና አውርተው አይጠግቡም፡፡ ያሰበበት ያበጃጀው ያደራጀው ሳይኖር በአጋጣሚ እንዲህ ሆኖ የመተለም (ዲሳይን የመደረግ) ዕድሉም ከዜሮ በታች ነው ብለውም ይመሰክራሉ፡፡

እንግዲህ ምን ማለቴ ነው ልብ ያለውና አስተዋይ ለሆነ ሰው እያንዳንዷ በአካባቢያችን ያለች ነገር ሁሉ ልብ ብሎ ለተመለከታት የፈጣሪን መኖር ትመሰክርለታለች፡፡ ደናቁርቱ ግን ይሄንን ማሰብ ማስተዋ መገንዘብ መረዳት ማጤን አይችሉምና ሁሉንም ቦታ አስሰው ፈልገው እንዳጡት ሁሉ አፋቸውን ሞልተው “ፈጣሪ የለም!” ሲሉ ትንሽም አይከብዳቸውም፡፡ የደንቆሮ ነገር ይሄው አይደል! በእነሱ ዘንድ ምንም ነገር ለማለት ድፍረት በሽ ነው፡፡

የተፈጠረ ነገር ሳይኖር “ፈጣሪ የለም!” ቢሉ ምንም ባልገረመኝ ባልደነቀኝ ነበር፡፡ ሰው እንዴት በዓይኑ የሚያየውን፣ በጆሮው የሚሰማውን፣ በእጁ የሚዳስሰውን፣ የተሸከመውን ነገር ዓይቶ አስተውሎ ማወቅ መረዳት መገንዘብ ይሳነዋል? የተፈጠረ፣ የተበጃጀ፣ የተደራጀ፣ የተቀመረ ነገር ካለ ማለት የሚቀለው “ፈጣሪ አለ!” ማለት ነው ወይስ “የለም!” ማለት? ከዚህ የከበደ ድንቁርናስ ምን አለ? አስቂኙና ማስተዋል የጎደለው አባባልስ የትኛው ነው? ለዚህም ነው ታላቁ ሳይንቲስት (መጣቂ) አንስታዩን “ፈጣሪ የለም!” የሚሉትን ሽባ ሲል የገለጻቸው፡፡

ይሄ ያልበሰለ ልጅ በመጽሐፉ በእግዚአብሔር ስላመኑ የዋሀን ሲል የሚጠራቸው ወገኖቻችን እሱ ያላንዳች ሐፍረት “ያወኩ የነቃሁ ነኝ!” የሚለው ሊያስተውለው ሊረዳው ያልቻለውን ከላይ የገለጽኩትን ሁሉ ትንግርት ልብ ብለው በማስተዋል ያለፈጣሪ እንዲህ ተሰካክቶ ሊቀመር ሊበጃጅ እንደማይችል በመረዳታቸው ነው “ፈጣሪ አለ!” ብለው ሳያወላውሉ ሊያምኑ የቻሉት፡፡ ቢያውቀው የዋሁ የማያስተውለውና ደንቆሮው እሱ እንጅ እነሱ አይደሉም፡፡

ሌላኛው የእግዚአብሔርን መኖር ያረጋግጣል የምለው አመክንዮ፡- መቸም ሰው ሆኖ የማይመኝ ሊኖር አይችልም፡፡ የሰው ጭንቅላት በተፈጥሮው እንዲሆን እንዲደረግለት እንዲያገኘው የሚፈልገውን እንዲመኝ ተደርጎ የተፈጠረ ነው፡፡ እኔ ተመኝቸ ፈልጌ አላውቅም የሚል ሰው ቢኖር እራሱን ሐሰተኛ ማድረጉ ነው፡፡ ጭንቅላቴ አያስብም ማለት ነውና፡፡ የሰው ልጅ እሱ ማድረግ ማግኘት ስላልቻለም ይሁን በሌላ ምክንያት የሚፈልገውን ነገር እንዲሆንለት እንዲያገኝ ይመኛል፡፡

ይሄ ማለት የምንመኘውን ነገር ሊያደርግልን የሚችል ኃይል አለ ማለት ነው፡፡ መቸም ምንም ነገር የሚያደርገው የሚከውነው ሳይኖር በራሱ አይፈጸምም አይሆንምና፡፡ ጭንቅላት ሲፈጠር የሚመኝ ሆኖ የተፈጠረው የሚመኘውን ነገር የሚፈጽም ኃይል ስላለ ነው፡፡ ጭንቅላት የሚመኘው ከምንም ተነሥቶ ሳይሆን የሚያደርገው አካል እንዳለ ስለሚያውቅ ነው የሚመኘው፡፡ ጭንቅላት ጤናማ በሆነ ሁኔታ እስካሰበ ጊዜ ድረስ ሊሆን የማይችልን የሌለን ሊፈጸም የማይችልን ነገር አያስብም አይመኝም፡፡

እናም እኛ በተለያየ ምክንያትና መንገድ በአቅም ውስንነት ተገትተንም ይሁን በሌላ ልናደርገው ልናገኘው ያልቻልነውን እንዲያደርግልን የምንጠብቀው ኃይል ያ ማለት ነው እግዚአብሔር ማለት፡፡ ይሄንን ስል መቸም ያን እንዲደረግልን የፈለግነውን ነገር እሱ እራሱ እግዚአብሔር ወርዶ ያደርገዋል ማለቴ አይደለም፡፡ በሆነ አካል ያድርና ነፍስ ያለውንም ግዑዙንም ነገር በመጠቀም ሁኔታዎችን በማሰካካት የተመኘነውን ነገር እንዲደረግ እንድናገኘው እንዲሆንልን እንዲፈጸምልን ያደርጋል እንጅ፡፡

ምን እያልኳቹህ መሰላቹህ የሰው ልጅ በዚህ መልኩ አቅመ ውሱን ሆኖ መፈጠሩ ይሄንን ክፍተቱን የሚሞላለት ኃይል (ፈጣሪ) መኖሩን ያሳያል፡፡ አቅመ ውሱንነቱ እራሱን በጭንቅ ጊዜ ከጭንቅ፣ በመከራ ጊዜ ከመከራ ለማዳን ለመጠበቅና እራሱን ከአደጋ ሥጋት ፍጹም ነጻ ማድረግ እንዳይችል አድርጎታል፡፡ ከድሮ ጀምሮ የሰው ልጅ እራሱ ለራሱ ይሄንን ማድረግ ካልቻለና ይሄንን የሚያደርግና እያደረገ ያለና የነበረ ኃይል ካለ በቃ! ያ ማለት ነው እግዚአብሔር ማለት፡፡

እናም ከዚህ ከዚህ በመነሣን ነገሩን በአስተውሎት ያየነው እንደሆነ “እግዚአብሔር የለም!” ማለት አለመብሰል መሆኑን መረዳት የሚቸግረን አይመስለኝም፡፡ ከላይ የጠቀስኩላቹህ ዓለም ያከበረቻቸው ታላላቅ ሰዎች በእግዚአብሔር ያመኑት ያሳይቡ ሳይመረምሩ የተረዱት ነገር ሳይኖር አይደለም፡፡

የዛኑ ያህል ደግሞ የእነዚህን የአማኞቹን ያህል ማሰብ መመርመር መረዳት ያልቻሉት ደግሞ ታላላቅ ሰዎች የሚባሉ ቢሆኑም የማያምኑ እንዳሉ ይታወቃል፡፡ ይህ አባባላቸው ስሜት ላይ እንጅ ዕውቀት ላይ የጠመሠረተ እንዳልሆነ ከላይ ላነሣናቸው አመክንዮዎች ምላሽ መስጠት የማይችሉ መሆናቸው ያረጋግጣል፡፡ ሁሉም ሊባሉ በሚችል ሁኔታ እነዚህ “እግዚአብሔር የለም!” ያሉ ዓለም ታላላቅ የምትላቸው ሰዎች “እግዚአብሔር የለም!” ያሉት ብዙ ሳይበስሉ ሳይመረምሩ ገና በወጣትነት ዕድሜያቸው ከዕድሜ ጋር ተያይዞ በሚመጣ ስሜት በመሸነፍ ለሃይማኖታዊ ሕግጋትና ለሞራል (ለቅስም) ድንጋጌዎች ላለመገዛት ላለመታዘዝና ስሜታቸው እንደወደደ መጠን “አጥፍታቹሀል! ኃጢአት ነው!” ሳይባሉ እነሱም “ደካማ ስለሆንኩ ተሸንፌ ሳይሆን በድንጋጌው ስለማላምንበት ነው!” በማለት ደካማ ተብለው ተወቃሽ ተከሳሽ እንዳይሆኑና ስሜታቸው ያዘዛቸውን የፈለጉትን ነገር ያለከልካይ እንዳሻቸው ለማድረግ ሲሉ ነው “እግዚአብሔር የለም!” የሚሉት፡፡

በወጣትነት ብዙ ሳያውቁ ሳይመረምሩ “እግዚአብሔር የለም!” ያሉ ፈላስፎች እድሜያቸው እየጨመረ ሲሔድ ከብዙ አቅጣጫ በሚያገኙት ዕውቀት ትምህርትና አስተውሎት እግዚአብሔር መኖሩን ቢረዱም ቢያውቁም ቢያረጋግጡም ያንን መመስከር አይፈልጉም፡፡ በፊት “የለም!” ብለው ስለነበረ አሁን “አለ!” ቢሉ እንደ አላዋቂና በስሜት እንደሚነዳ ማስተዋልና ኃላፊነት እንደጎደለው ሰው ስለሚያስቆጥራቸው ከጊዜ በኋላ በመጣና ባገኙት ዕውቀትና አስተውሎት ፈጣሪ መኖሩን ቢያውቁም ቢረዱም አለ ብለው አይመሰክሩም፡፡ የለም ብለው እንደደረቁ ይሞታሉ፡፡ እናም ወጣት “ፈላስፎች” አንዴ የያዙትን አቋም እስከመጨረሻው ይዘው የሚቀሩትና የመማር የመለወጥ ዕድል የማይኖራቸው በዚህ ምክንያት ነው፡፡

“እግዚአብሔርን በአካል ካላየነው በስተቀር አናምንም!” ከሆነ ጥያቄያቸው አዎ! በእርግጥ እግዚአብሔርን ማየት ይቻላል፡፡ የዩኒቨርስን (የፍጥረተ ዓለሙን) ስፋት ጥልቀትና ግዝፈት ተመልክታቹህ የዚህ ሁሉ ትንግርት ፈጣሪ ደግሞ ምን ያህል ሊያይል ሊገዝፍ ወይም ሊረቅ ማለትም ለማየት ከእኛ አቅምና ችሎታ በላይ ሊሆን እንደሚችል ማሰብ እንደሚገባ ታውቆ ማየት ከተፈለገ ግን እግዚአብሔር ከዚህ ቀደምም ለነቢያቱ ለሐዋርያቱ ለቅዱሳኑ ሲያደርገው እንደነበረው ሁሉ ልትረዱት በምትችሉት መጠንና አምሳል ተገልጦ ሊታያቹህ ይችላል፡፡ ይሁን እንጅ ለማየት ግን ቅድስና ያስፈልጋል፡፡ እንኳንና እግዚአብሔርን ሰይጣንን ለማየት እንኳን ቅድስና ያስፈልጋል፡፡ ሰይጣን ውዳቂ ምናምንቴ ስለሆነ ለሁሉም ዓይታይም፡፡ በእርግጥ ለጠንቋዮች ማለትም ለአገልጋዮቹ ይታያል፡፡ እየጠነቆሉ በሚያደርጉት ነገር እሱን ስለሚያገለግሉት፡፡ ለመገልገል ለማዘዝ እንዲመቸው ለነሱ ይታያቸዋል፡፡

አሁን ወደ በውቀቱ እንለፍ፡፡ አንዴ ከዓመታት በፊት ነው ቆይቷል በውቀቱ ሥዩም በአቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ላይ እየተሳለቀ “…የእኛ አባቶች ለተጠማ ወፍ ዓይናቸውን አፍስሶ ውኃ እንዲጠጣ የሚፈቅዱ የዋሀን ናቸው…” በማለት ስላፌዘ ደወልኩለት፡፡ እንደምታውቁት በውቀቱ ፍጹም አመክንዮአዊና ሥርዓት በሌለው፣ ሞያዊ አኪያሔድ ባልጠበቀ መንገድ፣ ሚዛናዊነት የሚባል ዕይታ ጨርሶ በሌለው ዓተያይ በቅዱሳንና በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እሴቶች ላይ እያፌዘና እየቀለደ ያለ፤ በዚህም መታወቅ የሚፈልግና ይሄንን በማድረጉም እንደፈላስፋ ለመቆጠር የሚመኝ የሚጥር ግለሰብ ነው፡፡

እናም ከዓመታት በፊት የገና ዕለት ደወልኩለት፡፡ ከላይ የጠቀስኩትን ቃል አስታወስኩትና በዚህና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ እንድንነጋገር ፈልጌ እንደደወልኩለት ነገርኩት፡፡ ለመነጋገር ፈቃደኛ እንደሆነ ገለጸልኝና ለረጅም ሰዓታት አወራን፡፡

ቅድሚያ ያነሣነው ጉዳይ የነበረው “እንዲህ ዓይነት ነገሮችን መናገር ፈላስፋነት ይመስልሀል ወይ?” ብየ የጠየኩትን ጉዳይ ነበር፡፡ እሱም ፈላስፋ ለመሆን ሳይሆን የታየውንና ትክክል ነው እውነት ነው ብሎ የማያምንበት ነገር ሐሳብን የመግለጽ ነጻነቱን በመጠቀም እንደገለጸ ነገረኝ፡፡ እኔም “አይ ይሄ እማ ከሆነ እራስህን ወንጀለኛ አድርገሀል ማለት ነዋ! እኔ መስሎኝ የነበረው እራስህን እንደፈላስፋ ቆጥረህ በፈላስፋነት ያለውን ነጻነት ተጠቅመህ ለመተቸት ለመሔስ አስበህ የምትናገር አድርጌ ቆጥሬህ ከተናገርከው አንጻር ፍልስፍና ማለት ምን ማለት እንደሆነ ለመነጋገር ነበር ያሰብኩት፡፡ እንዲህማ ከሆነ የፈላስፋነት ከለላም አይኖርህም ተራ ወንጀለኛ ሆንክ ማለት ነው” ስለው “የተናገርኩት ከፍልስፍና አንጻር ማየት አይቻልም?” ሲል ጠየቀኝ “ከፍልስፍና አንጻር ለማየት አይደለም ስላልክ ከሱ አንጻር ነበር ወንጀለኛ ነሀ ያልኩት፡፡ ምንም ነገርን መተቸት የለብህም” ማለቴ እንዳልሆነ ገልጨለት ሲተች ግን ሞያዊ የትችት ወይም የሒስ አሰጣጥ ዘዴን መከተል እንደሚኖርበት፣ ከዚህ አንጻር ይህ ስለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የተናገረው ነገር እንደሌሎቹ በእሴቶቻችን ላይ የሚናገራቸው ነገሮች ስድነት የሚታይባቸው ተራ የጥላቻ ወሬ መሆኑን ይሄም ትዝብትና መገመት ላይ እንደሚጥለው ለማስረዳት ሞከርኩ፡፡

እሱም ይህ የተናገረው ነገር ሞያዊ የሚሆነው እንዴት ቢሆን እንደነበረ ጠየቀኝ፡፡ እኔም አነጋገሩ የፍልስፍናን የመከራከሪያ አኪያሔድና ስልት የተከተለ የጠበቀ እንዳልሆነ ስነግረው “እንዴት?” ሲል ጠየቀኝ “ጥሩ” በማለት ይሄን ወደ ኋላ እንደምናየው ነግሬው አሁን ግን አንተ “የመናገር ነጻነትን መብት ከመጠቀም አንጻር ነው የተናገርኩት” ብለሀልና ከዚህ አንጻር የተናገርከው ነገር እንዴት ስሕተት እንደሆነ እናውራ አልኩትና በዚሁ ጉዳይ አወራን፡፡

ይሄውልህ በውቀቱ እርግጥ ነው አንተ እንዳልከው አንድ ሰው ሐሳቡን በነጻነት የመግለጥ ተፈጥሯዊ መብትና ነጻነት አለው፡፡ ፖለቲከኞች (እምነተ አሥተዳደራዊያን) ይሄንን መብት ከዲሞክራሲያዊ (ከመስፍነ ሕዝባዊ) መብቶች አንዱ እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡ ይሁን እንጅ የሰው ልጅ ማኅበራዊ ፍጡር (እንስሳ ላለማለት ነው) እንደመሆኑ ምንም እንኳን ሐሳብን በነጻ የመግለጥ ነጻነት ቢኖረውም ያ የሚናገረው ነገር የሌሎቹን መብት የሚጥስ የሚጋፋ የሚያጠቃ ከሆነ መብት መሆኑ ቀርቶ ወንጀል ይሆናል፡፡ እንደ ማኅበራዊ ፍጡርነታችን ሐሳብን በነጻ የመግለጥ መብት የጋራ ጥቅማችንን ከመጉዳት ከማጥቃት በመለስ ያለ መብት እንጅ ሥርዓትና አግባብነት በሌለው መንገድ እንደፈለግን የሌሎችን መብት ማንነትና ጥቅም ልናጠቃ የምንችልበት መብት አይደለምና፡፡

አልኩትና አቶ ዓለማየሁ ሞገስን (በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ወይም መካነ ትምህርት መምህር የነበሩ) ምሳሌ አድርጌ አቀረብኩለት፡፡ አቶ ዓለማየሁ ሞገስ እስላሞች ነቢያችን ናቸው የሚሏቸውን መሐመድን “ለምን አልሰለምኩም” በሚለው መጽሐቸው ለመግለጽ የሚቀፉ ድርጊቶችን እየዘረዘሩ “እንዲህ እንዲህ ያደረገ ነው” እያሉ ክፉኛ አበሻቅጠው አዋርደው ስለነበር እስላሞች ተጠቃን ተደፈርን ተዋረድን ብለው መክሰሳቸውን በማስታወስ ፍርድቤቱም ክሱን ትክክል ነው ብሎ ተቀብሎት እንደነበር፤ አቶ ዓለማየሁ ሞገስም “ለጠቀስኳቸው ነገሮች ሁሉ ማስረጃ ማጣቀሻዎች አሉኝ” ብለው የነ ሳልማን ሩሽኪን (ኢራን እሱን ለገደለ አምስት ሚሊዮን ዶላር እሸልማለሁ ስትል የሞት አዋጅ ያስነገረችበት ኢንግሊዛዊ ደራሲ) እና ሌሎች መሐመድ ላይ የተጻፉ መጽሐፍትን በመከላከያ ማስረጃነት አቅርበው ጉዳዩ እየታየ እንዳለ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ክሱ እንደተቋረጠ በማንሣት ቤተክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ ሥራውን በአግባቡ የሚሠራ ተቆርቋሪ አካል ስለሌላት እንጅ እሱ የሚናገራቸው ነገሮች ተራና መረጃ የሌለው ስም ማጥፋትና ክብር መዳፈር ስለሆኑ ሊያስከስሱት ይችሉ እንደነበር ገለጽኩለት፡፡

እሱም በሀገራችን ነው እንጅ እንዲህ ዓይነቱ ነገር ያልተለመደው በሠለጠነው ዓለም ግን እንዲህ ዓይነት ሒሶችና ትችቶች በነጻነት እንደሚሰጡ ተናገረ፡፡ እኔም “ልክ ነህ ግን አንተ በተረዳህበት መንገድ አይደለም” ስል ገልጨ ከላይ ወደ ኋላ እናየዋለን ወዳልኩህ ጉዳይ መግባታችን ነውና ወደዚያው ልግባ ብየ “እርግጥ ነው በሠለጠነው ዓለም እንዲህ ዓይነቱ ነገር የተለመደ ነው፡፡ ይሁንና ሁሉም ሞያዊ አኪያሔድና አሠራር የተከተሉ አይደሉም ይሄም በመሆኑ ጥቂት የማይባሉ ትችቶች በእምነት ተቋማቱ ክስ እንደመተመሠረተባቸው ከፊሎቹ ደግሞ የአተያው ልዩነት ቢኖርም ሞያዊና በመረጃ የተደገፉ በመሆናቸው የእምነት ተቋማት ባይወዷቸውም ክስ ያልመሠረቱባቸው እንዳሉ ገለጽኩለት፡፡

ከዚህም ጋራ አያይዠ እሱ በአቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ላይ የተናገረው ነገር እንዴት ሞያዊ አኪያሔድን የተከተለ እንዳልሆነ ልገልጽለት ሞከርኩ፡፡ እንዲህ በማለት፡- አስቀድሜ “ሃይማኖትህ ምንድን ነው?” ስል ጠየኩት፡፡ ሃይማኖት እንደሌለውና በእግዚአብሔር እንደማያምን ቀደም ሲል ያልመረመረና አላዋቂ በነበረ ጊዜ ግን ኦርቶዶክስ እንደነበረ ነገረኝ፡፡ እኔም እሽ አስቀድመህም ከፈላስፋ አንጻር ትችቱን እንዳልሰጠህ ነግረኸኝ ነበር ከዚህ አንጻር ለማየት የሚያበቃ ብቃት ስለሌለው ስልህ እንዴት አይችልም ብለኸኝ ነበር እሱን አሁን እነግርሀለሁ፡፡ የተናገርከውን ልብ በል “የእኛ አባቶች ለተጠማ ወፍ ዐይናቸውን አፍስሶ ውኃ እንዲጠጣ የሚፈቅዱ የዋሀን ናቸው…” ነው ያልከው፡፡ “አባባልህ በሙሉ ልቡ ያላመነ የተጠራጣሪ አማኝ አባባል እንጅ የፈለስፋ አይደለም” ስለው “እንዴት?” አለኝ “አባባልህ የአቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስን ገድል ከፊል አምነህ ተቀብለሀልና፡፡ ለማለት የፈለኩት ገድላቸው ላይ እንዳለው አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ በወፍ ተመስሎ ለመጣው ሰይጣን ውኃ ሳያጣ ሲጠማው ሊጠጣ የሚችልበትን ሐይቁን ትቶ ምን ፈልጎ በምን ምክንያት ውኃ እንደጠየቃቸው ስለሚያውቁ የዓይናቸውን ውኃ እንዲጠጣ ስለመናገራቸው ገድላቸው ላይ የተጻፈውን አምነሀል፡፡ ይሄንን አምነህ የተናገርከውን ከተናገርክ በኋላ እንደገና ደግሞ ከዛ ወጥተህ ድርጊቱን ቂልነት ነው ልትል የምትችልበትን መሠረት ልታገኝ አትችልም፡፡ አባታችን ከዓይናቸው እንድትጠጣ መፍቀዳቸውን ቂልነት ነው ካልክ የወፏን በሰው አንደበት ተናግራ ውኃ አጠጡኝ ማለቷን ልታምን አትችልም፡፡ ስለዚህ በፈላስፋ ቦታ ሆነህ “ለተጠማ ውኃ ዓይናቸውን አፍስሶ እንዲጠጣ የሚፈቅዱ የዋሀን” በማለት ልትሳለቅ አትችልም ማለት ነው፡፡

የፈላስፋን የመተቸት መሠረት ወይም ሞያዊ አኪያሔድ የተከተለ አይደለም ያልኩህም ለዚህ ነው፡፡ ቀሽም ተች የሆንከውም ለዚህ ነው፡፡ ከፊሉን አምነህ ከፊሉን ለመተቸት በመሞከርህ፡፡ ሊሆን አይችልም ካልክ አለቀ በቃ ሊሆን አይችልም ወፏ በሰው አንደበት ተናግራ ውኃ አጠጡኝ ማለቷንም ማመን የለብህም፡፡ ይሄንን ካመንክ ደግሞ እሳቸው ወፏን ያስተናገዱበትን መንገድም ልትተች አትችልም፡፡ ካመንክ እንደ ተአምርነቱ ሁሉንም ማመን ይኖርብሀል ካላመንክም ሁሉንም አለማመን ይኖርብሀል፡፡ አንተ ከሁለቱም የለህም፡፡ በመሆኑም ያቀረብከው ሞያዊ አኪያሔድን የተከተለ ፈላስፋዊ ትችት ሳይሆን ሥነ ምግባር የጎደለው ስድ የደንቆሮ አባባል ነው፡፡ ከሁሉም የሌለ አንተነትህን ማንነትህን ብቻ የሚያሳይ ወንጀለኛ አነጋገር ነው፡፡ ስል መለስኩለት፡፡

በመቀጠል ለምን በእግዚአብሔር ከማመን ወደ አለማመን እንደተሸጋገረ ጠየኩት፡፡ እሱም “አይ! እግዚአብሔር የሚባል ነገር ስለሌለ፤ እግዚአብሔር የሚለውን አካል የፈጠሩት ሰዎች መሆናቸውን ስላወኩና በእግዚአብሔር ማመን ሞኝነት ቂልነት ስለሆነ ነው” አለኝ፡፡ እኔም “ጥሩ እግዚአብሔር አለመኖሩን እንዴት አረጋገጥክ? መሬቱንም ሰማዩንም አጠቃላይ ፍጥረተ ዓለሙን (ዩኒቨርስን) ፈትሸህ ስላጣኸው ነው? እንኳንና አንተ ጠፈርተኞችም እንኳን ገና ከማርስ አላለፉም በመንኮራኩር ጥቁር ጉድጓድን (ብላክ ሆልን) ለመሻገር ብቻ እንኳን በብዙ ሚሊዮን (አእላፋት) ዓመታት እንዲሚያስፈልግ ነው የሚናገሩት፡፡ አንተ ታዲያ ከጎጃምና ከአዲስ አበባ ሳታልፍ መላ ፍጥረተ ዓለሙን አስሰህ እንዳጣኸው ሁሉ እንዴት እግዚአብሔር የለም ትላለህ?” ስል መልሸ ጠየኩት፡፡ ሊመልሰው የቻለው ነገር አልነበረም፡፡

ቀጠልኩና ሲጀመር እንዲያው አባባልህ ምን ያህል የተሳሳተ እንደሆነ እንድትረዳና እራስህን እንድትታዘበው ይሄንን አልኩህ እንጅ እግዚአብሔር እንደ ዕቃ ተፈልጎ የሚገኝ ነገር አይደለም፡፡ እግዚአብሔርን ለማየት ወይም መኖሩን ለማረጋገጥ የሚቻለው በእምነት መንገድ ነው እንጅ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ አይደለም ማረጋገጥ የሚቻለው፡፡ ስለሆነም የትኛውንም መንገድ ተጠቅመህ ፈትሸህ ሳታረጋግጥ የለም ማለትህ እጅግ ግብዝና አላስተዋይነትህን እንጅ በሳል መርማሪነትህን አይደለም የሚያሳየው ስለው፡፡ እኔ በሱላይ የተጠቀምኩትን አመክንዮ በእኔ ላይ መጠቀም ፈለገና “አንተ በእግዚአብሔር ታምናለህ?” ሲል ጠየቀኝ “አዎ! በሚገባ ነዋ!” ስል መለስኩለት፡፡ ቀጠለና “አንተ በእግዚአብሔር ያመንከው መኖሩን አረጋግጠህ አይተኸው ነው?” ሲል ጠየቀኝ፡፡ እኔም “አዎ” ስል መለስኩለት፡፡ እሱም “እንዴ! እንዴት ሊሆን ይችላል? ልታረጋግጥልኝ ትችላለህ?” ሲል ጠየቀኝ “በሚገባ” ስለው “አይ! በቃ መቀለድህ ነው መሰለኝ” አለኝ፡፡ እኔም “ኧረ እኔ እውነቴን ነው እንዲህ ባለ ቁምነገር ላይ ቀልድ አለ እንዴ!” ስለው “እና ምን እያለከኝ ነው?” አለ፡፡

እኔም ““ልብ ብለህ አድምጠኝ በውቀቱ፤ ቆይቷል ከዓመታት በፊት እኔም እንዳትተ ክህደት ጠልፎኝ “መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ምድር በምድር ስላሉ ፍጥረታትና ስለሌሎች ዓለማት የሚሰጠው ምንም ዓይነት በቂ መረጃ የለም! እውነተኛ የእግዚአብሔር ቃል ቢሆን ኖሮ ስለ እግዚአብሔር ፍጥረታት ሁሉ በቂ መረጃ ይሰጥ ነበር በቃ! ይሄ ውሸት ነው…” በማለት የእግዚአብሔርን መኖር ተጠራጥሬ ለመፈጥፈጥ እየወረወርኩ የነበርኩበት ወቅት ላይ ሆኘ ለሥራ ጉዳይ ለሀገሩ እንግዳ ለሰው ባዳ ወደ ሆንኩበት ሀገር ሔጀ ነበረ እዚያ ቦታ ላይ የክህደት አስተሳሰቤን እንደጉም አብንኖ እንደጢስ አትንኖ ያጠፋልኝ አንድ አጋጣሚ ተከሰተ፡፡

ለሥራ በሔድኩበት ሀገር እንዳልኩህ የማውቀው የሚያውቀኝ የሌለበት ቦታ ነው፡፡ እዚያ ሀገር እንደገባሁ በማግስቱ ከአካባቢው ሰው ጋር ሆኘ አካባቢውን ስጎበኝ የጸመል ቦታ ላይ ደረስኩ፡፡ ከጸበሉ ቦታ ላይ ተጸባዮች (ተጠማቂዎች፤ ተጠመቀ የሚለው ቃል በአርባና በሰማንያ የምናገኘውን የእግዚአብሔር ልጅነት ለመግለጽ ስለምንጠቀምበት ለዚህኛው ጉዳይ ተጸበለ የሚለው አማርኛ ተስማሚ ነው) ነበሩ፡፡ ከተለያየ ሕመም ወይም ደዌ ለመፈወስ የሚጸበሉ ነበሩ ካደረባቸው እርኩስ መንፈስ ለመላቀቅ ለመገላገል የሚጸበሉም ነበሩ፡፡

እኛ ከቦታው ስንደርስ ክፉ መንፈስ ካደረባቸውና ሲጸበሉ ያደረባቸው ይሄ ክፉ መንፈስ ይለፈልፍባቸው ከነበሩ ተጸባዮች በአንዷ ላይ የሚለፈልፈው ጋኔን እኔን በስሜ እየጠራ “የኛ ፈላስፋ! እግዚአብሔር የለም አይደል?” እያለ ከልጅነቴ ጀምሮ የተረፍኩባቸውን ለሞት የሚያበቁ አደጋዎችን እያስታወሰ “ከዚህ ከዚህ ያዳነህ ያተረፈህ ያወጣህ ማን ነበረ? አንተ ከሀዲ!” እያለ ይዘልፈኛል፣ እኔ እና እግዚአብሔር ብቻ የምናውቀውን ምሥጢርና የሠራሁትን ኃጢአቴንም ጭምር እየተናገረ ከዚያ ሁሉ ሰው ፊት አዋረደኝ፡፡ መሬት ተከፍታ ብትውጠኝ በወደድኩ፡፡ እዚያ የጸበል ቦታ ላይ እንዲያ ከመዋረዴ የተነሣ ልገልጸው በማልችለው መልኩ እጅግ ቀልየ ብዙ መቆየት ስላልፈለኩ ወዳረፍኩበት ቤት ወዲያው ነበር የተመለስኩት፡፡ ይህ ሁኔታ እዚያ ሀገር የወሰደኝ የሥራ ጉዳይ የጥቂት ቀናት ቢሆንም ከሚገባው በላይ አሳጥሬ ቶሎ ወደ መኖሪያዬ እንድመለስ ስላስገደደኝ ቶሎ ተመለስኩ፡፡

ይህ አጋጣሚ ነበር አሁን አንተ እንደምትለው ሁሉ ተፈላሰፍኩ ተመራመርኩ ብየ “እግዚአብሔር የለም!” ከሚለው ክህደቴ መልሶ በሃይማኖት እንድጸና ያደረገኝ፡፡ ከዚያ በኋላማ ገዳማት ውስጥ ከተጋድሏቸው የተነሣ ለዚያ ጸጋ ከበቁ ቅዱሳን አባቶች ጋር በመገናኘት የነቢይነትን ጸጋ እንደማግኘታቸው ያሳለፍኩትንና የሚገጥመኝን እየነገሩ በመገሰጽና በማስጠንቀቅ ማወቅ የተፈቀደችልኝን ያህል እየነገሩም ሕይዎቴን አንጸውታል፡፡ ባገኙት ጸጋ ፈጣሪን በእነሱ ውስጥ ዓይቸዋለሁ መኖሩንም በዚህ መልኩ አረጋግጫለሁ፡፡

“መጽሐፍ ቅዱስ እውነተኛ የእግዚአብሔር ቃል ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔር ስለፈጠራቸው ፍጥረታት ሁሉ ስለ እያንዳንዱ ነገር በቂ መረጃ ይሰጠን ነበር” ብየ እራሴ አንሥቸ እራሴ የተሰናከልኩበት ጥያቄም ማንም ሳይመልስልኝ መጽሐፍ ቅዱስ አሁን ባለበት መልኩ የተጻፈው “ለአዋቂ አንዲት ቃል ትበቃዋለች” እንዲሉ በጥቁምታ ደረጃ እግዚአብሔር የሚባል አምላክ ፈጣሪ መኖሩን ለማሳወቅ ያህል መጻፍ የነበረበትና የተጻፈ ቅዱስ መጽሐፍ እንጅ ስለ አጠቃላይ ፍጥረተ ዓለም (ዩኒቨርስ) ይጻፍ ይዘርዝር ያስረዳ ቢባል ወንጌላዊው ዮሐንስ እንዳለው “ኢየሱስም ያደረገው ብዙ ሌላ ነገር ደግሞ አለ፡፡ ሁሉ በእያንዳንዱ ቢጻፍ ለተጻፉት መጻሕፍት ዓለም ራሱ ባልበቃቸውም ይመስለኛል” ዮሐ. 21፤25 እንዳለው ሁሉ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር ሥራ ብቻ ሳይሆን ስለፈጠረው እያንዳንዱ ነገር ሁሉ ይናገር ቢባል መጽሐፉ መጽሐፍ መሆኑ ቀርቶ ሰማይ ጥግ ድረስ የሚደርስ እጅግ ግዙፍ ተራራ የሚያክል ሊሆን እንደመቻሉ የሚታሰብ ነገር አይደለምና ይሄ ሐሳቤ ትክክለኛ ጥያቄ አለመሆኑን ከእራሴ አመክንዮ ተረድቸ ተሰበሰብኩ እልሀለሁ በውቀቱ፡፡ ስለዚህች ዓለም ጉዳዮች የሚያትቱት የትምህርትና የምርምር ውጤት መጻሕፍት እንኳን ምን ያህል እንደሚበዙ አስብ፤ እኔ እያልኩ የነበርኩት መጽሐፍ ቅዱስ እነሱ የተናገሩትን ሁሉ መያዝ ነበረበት ነው እያልኩ የነበርኩት፡፡ አየህ ምን ያህል ቂል እንደነበርኩ?

በእርግጠኝነት አንተም ጸበል ቦታ ብትሔድ የግድ እኔ ሔጀበት ወደነበርኩበት ቦታ ማለቴ አይደለም የትኛውም ጸበል ቦታ ብትሔድ እግዚአብሔር ለአንተ በሚገባህ አንተ በምትረዳው መልኩ ተመሳሳይ ነገር አድርጎ ህልውናውን ወይም መኖሩን ያረጋግጥልሀልና ጸበል ሒድ፡፡ በሚገርም ሁኔታ የጸበል ቦታዎች እዚያ በሚሠሩ ተአምራቶች የእግዚአብሔር መኖር የሚረጋገጥባቸው (ፕሩፍ የሚደረግባቸው) ቦታዎች ናቸው፡፡ እንኳን የጸበል ቦታ የጠንቋይ ቤት እንኳን እግዚአብሔር መኖሩ የሚታወቅበት ቦታ ነው፡፡ እዚያ ቦታ ላይ ሰይጣን በጠንቋዩ አድሮ የሚያደርገውን የክፋት ሥራና የሚሠራውን ተአምራት በማየት የማተካካትን (የሰብስቲቲዩሽንን) አመክንዮ በመጠቀም (A=B=C\A=C) በሚለው አካሔድ “ሰይጣን አለ ማለት ተቃራኒው እግዚአብሔር አለ ማለት ነው!” ብሎ በማሰብ የእግዚአብሔርን መኖር ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ብየው እሱም በሆነው ነገር ተገርሞ “እሽ እሔዳለሁ!” ብሎኝ ነበር፡፡ ስንለያይም ስምህን አውሰኝ (አስተዋውቀኝ ማለቱ ነው ነገር ግን አውሰኝ የሚባለው ተገልግለንበት ለምንመልሰው ነገር ነውና የቃሉ አጠቃቀም ስሕተት ነው) ብሎኝ ስሜን ነግሬው ተለያየን፡፡

እናም ከዓመታት በፊት የጌታ ልደት በዓል በሚከበርበት ቀን ለበውቀቱ ደውየለት ይሄንን ነበር ያወራነው፡፡ አሁን ከልጁ “ከአሜን ባሻገር” ከሚለው መጽሐፉ እንዳየሁት ግን ምክሬን ሰምቶ እሽ ብሎኝ የነበረውን እንዳልፈጸመ ነው፡፡ ለምን እንዳልፈጸመም አላውቅም ወይም እንግዲህ “እግዚአብሔር የለም!” ማለትንና የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እሴቶችን እያዋረደ እየዘረጠጠ መኖርን እንጀራው አድርጎት ይሄንን ማጣት ስላልፈለገም ሊሆን ይችላል ልጁ አሁንም ባለበት የክህደት ዓለም ውስጥ ነው ያለው፡፡ ለነገሩ ይሄ ክህደቱና ቤተክርስቲያንን የማጥቃት የመዋጋቱን ነገር እያደረገ ያለው ካደረበት ጋኔን የተነሣ ነውና ደኅና ዘመድ ካልወሰደው በስተቀር እንደመከርኩት ሁሉ በራሱ ተነሣሽነት ወደ ጸበል ይሔዳል ብሎ ማሰብ የማይታሰብ ነው፡፡ ይሄንን የሚያደርገው ካደረበት ጋኔን የተነሣ ስለሆነም ነው ብቸኛው ማረጋገጫ ነው ማለት ባይቻልም ልጁ አፉን የሚከፍተው በአንዲቷ ቤተክርስቲያን ላይ ብቻ እንጅ በእስላሞችና በመናፍቃን ላይ ትንፍሽ የማይለው፡፡ እንደ ከያኔ የከያኔነት ኃላፊነት ተሰምቶት የሚያየውን የሚያስተውለውን የሚሔስ የሚተች ቢሆን ኖሮ በመናፍቃኑና በእስላሞች ላይ ስንትና ስንት ሊለው የሚችለው ነገር ነበር፡፡

ይሄ ካልሆነ በስተቀር ለዚህች ሀገር ሁለንተናዊ ማንነት ከነጻነቷ እስከ ብርቁና ድንቁ ጥንታዊ ሥልጣኔዋ ድረስ ብቻዋን ስትፈጋ የነበረችን፣ ስንት ተነግረው የማያልቁ ትሩፋቶችን ያበረከተችን ቤተክርስቲያን፣ በመንግሥት አሥተዳደርም የከፋ ሲመጣ አባብላ ጫና ሲመጣባት እያቻቻለች ይህችን ሀገር ከሕዝቧ ጋር የተቻላትን ሁሉ በማድረግ ጠብቃ የኖረችን ቤተክርስቲያን ይሄንን ሁሉ ውለታዋን ገደል ከቶ ጥቃቅን ነገር እየጠቃቀሱ መኮነን፣ ለማዋረድ ዋጋ ለማሳጣት ጥረት ማድረግ ከድንቁርና የመነጨ ወራዳ ተግባር ወይም ለጠላት ቅጥረኛ ሆኖ ሥውር የባንዳነት ተልእኮን መፈጸም ካልሆነ በስተቀር በምንም ተአምር አግባብነት ያለው ተግባር ሊሆን አይችልም፡፡

አለማወቁ ነው እንጅ ይህች ቤተክርስቲያን በፍጹም በፍጹም እሱ በሚያስባት መልኩ የምትከሰስ አይደለችም፡፡ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከስድስት መቶ ዓመታት በፊት በአባ ማስያስ ገድል ላይ “ዓለም እንደጋን ድቡልቡል ናት ጠፍጣፋ አይደለችም!” ስትል የምዕራቡ ዓለም ስቆብን አፊዞብን ነበር፡፡ እነሱ ይሄንን እውነታ ለማረጋገጥ ዘመነ ቴክኖሎጂን (ኪነብጀታን) መጠበቅና ወደ ሕዋው መጥቆ ማረጋገጥ ግድ ነበረባቸው፡፡ እንዲህ ዓይነት በርካታ ነገሮች ሳይንስ (መጣቅ) የራሱ ግኝት አድርጎ የሚያወራቸው የቤተክርስቲያን ዕውቀቶች በርካታ አሉ፡፡ በሥነፈለኩ (በሕዋው ምርምር) ሳይንስ (መጣቅ) እስካሁን ከተጠቀመበት የቤተክርስቲያናችን ዕውቀት ይልቅ ገና ያልደረሰበት ይበዛል፡፡

ምዕራባዊያ ሀገራት ከሽህ ዓመታት በፊት ጀምሮ የእኛን የብራና መጻሕፍት የመዝረፍ እሽቅድድምና ሽሚያ ውስጥ የተጠመዱት ያለአንዳች ጥቅም አይደለም፡፡ በየ ዩኒቨርስቲያቸው (መካነ ትምህርታቸው) ዜጎቻቸውን የግእዝ ትምህርትን የሚያስተምሩት ለእኛ ቋንቋ ፍቅር ስላላቸው ሳይሆን እየዘረፉ የወሰዷቸውን መጻሕፍቶቻችን የያዟቸውን ዕውቀትና ጥበቦች ለመቦጥቦጥ ለመበዝበዝ ነው፡፡

የምዕራቡ ዓለም የመድኃኒት ፋብሪካዎች መድኃኒት ማምረትን ሲጀምሩ ብቸኛ የዕውቀት ምንጫቸው የነበረው የእኛ የብራና መጻሕፍቶቻችን መሆናቸውን እራሳቸው ይናገራሉ፡፡ የጀርመኑን ባየር መድኃኒትና ኬሚካል (ምዝ) አምራች ድርጅትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ይህ ድርጅት በዓለም በፈዋሽነታቸው ታዋቂ የሆኑ መድኃኒቶችን በማምረት ይታወቃል፡፡ ይህ ድርጅት መጀመሪያ ላይ ያመርታቸው የነበሩትን መድኃኒቶች ያመርት የነበረው ስለ እጽዋትና ጥቅማቸው የሚተነትን ጥንታዊ የግእዝ መጽሐፍ የሰጠውን ዕውቀት በመጠቀም እንደሆነ እራሱ ድርጅቱ መጽሐፉን በድርጅቱ የእንግዳ መቀበያ ክፍል ላይ በመስታውት ሳጥን ላይ በክብር አስቀምቶ በማስጎብኘት ጭምር የሚመሰክረው ሐቅ ነው፡፡

ከምናውቀውና ከማናውቀው ይህች ሀገር ከምትታወቅባቸው ከዚህች ሀገር ወጥቶ ዓለም ከተጠቀመበት የሥልጣኔ ፍሬያችንና ብርቅየ እሴቶቻችን ውስጥ ከእሷ ያልወጣ የእሷ ያልሆነ አንድ ነገር እንኳን መጥቀስ አንችልም፡፡ ይሄንን ያህል ለዓለም ሥልጣኔ የማይተካ ሚና የተጫወተችን ቤተክርስቲያን እንደ ምናምንቴ ቆጥሮ ማዋረድና መዘርጠጥ እንድትናቅም ጥረት ማድረግ ድንቁርና አይደለም ካላቹህ ባንዳነት ለመሆኑ ምንም የሚያጠራጥር ነገር አይደለም፡፡ ለነገሩ ልዩነት የላቸውም፡፡ ደንቆሮ ሁሉ ባንዳ ነው ባይባልም ባንዳ ሁሉ ግን ደንቆሮ ነው፡፡

ሲጀመር አንድ ሰው አንድን አካል መተቸት ስለተፈለገ ብቻ አይተችም፡፡ ለመተቸት ከመነሣታችን በፊት ማንን እንደምንተች፣ ምን እንደምንተች፣ ለምን እንደምንተች፣ እንዴት እንደምንተች ጠንቅቀን ማወቅ ይጠበቅብናል፡፡ አንድ አካል በሁለት መንገድ ይተቻል፡፡ አንደኛው ያ አካል አርአያነት የሌለውና ጎጂ አጥፊ መሆኑን ከማስረዳት ከማረጋገጥና ሕዝብና ሀገርን ከዚህ ጎጂ አካል እንዲጠበቁ እንዲርቁ ለማብቃት ከማሰብ አንጻር ይተቻል፡፡ ይሄንን አካል በዚህ ተግባር ለመፈረጅ ከሠራው ሥራ ያጠፋው ካለማው የሚበልጥ የሚበዛ ወይም ከሞላ ጎደል ሥራው ተግባሩ የጥፋት መሆን ይኖርበታል፡፡ ይሄኔ ይህ አካል “በውጉዝ ከመ አርዮስ” ቅኝት ይወገዛል ይኮነናል ይጣጣላል ይብጠለጠላል፡፡

ሌላኛው መንገድ ደግሞ ያ አካል ጠቃሚ በጎ የሚበጅ ሥራ የሠራ ሆኖ እያለ መቸም ቢሆን የትም ፍጹም ሆኖ መገኘትና መቶ በመቶ ከእንከን የጸዳ ፍጹም የሆነ ሥራ ሠርቶ መገኘት ከቶውንም አይቻልምና ከዚህ ውስንነት የተነሣ አንዳንድ ጥፋቶች እንከኖች ሲገኙበት እንዲያው “ይህቺ ይህቺ ነገር ባትፈጸም ኖሮ እንዴት ጥሩ ነበር!” ለማለት ለመማሪያ ያህል ትንኝ እንደማጥራት ያለ የመተቸት ተግባር ይሠራል፡፡ ምን እናውራ ከሚል በዚህ የትንኝ ማጥራት ዓይነት ትችት ለመተቸት የሚበቃው አካልም በዚህ ቦታ ወይም መገለጫ ለመፈረጅ ከሠራው ሥራ ያጠፋው ጥቂት መሆንና ያለማው የሚበዛ መሆን ይኖርበታል፡፡

አሁን ታዲያ ይሄ ሰው የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን “በውጉዝ ከመ አርዮስ” ቅኝት እየተቸ፣ እያወገዘ፣ እየተቃወመ፣ እያብጠለጠለ ያለው ቤተክርስቲያኗ ለዚህች ሀገር ሁለንተናዊ ማንነት ካበረከተችው አንጻር ያጠፋችው ካለማችው በዝቶ ይሄ በርካታው ክፉው ሥራዋ ጥቂቱን መልካሙን ሥራ ውጦት ነው ቤተክርስቲያኗን ታጥቆ እያጠቃ ያለው??? ነው ወይስ ማን? እንዴት ባለ መንገድ? ለምን? እንደሚተች እንደሚሔስ ጨርሶ ምንም የሚያውቀው ነገር ስለሌለው ምናልባትም ከአስተዳደጉ ባዳበረው ኢግብረገባዊ ጠባይ በመገፋፋት ነው አፉ እንዳመጣለት ስድና ግብረገብነት በጎደለው መልኩ ሊያዋርዳት ጥረት እያደረገ ያለው?

እርግጥ ነው አሁን ሀገራችን ያለችበት ሁኔታ ቤተክርስቲያን ከሐዲስ ኪዳንም ከብሉይ ኪዳንም በፊት ከጥንት ከሕገ ልቡና ጀምራ (በዚያን ጊዜም ቤተክርስቲያን ትባል ነበር ማለቴ አይደለም) ለዚህች ሀገርና ሕዝብ ያደረገችውን ጥረት ድካምና ልፋት አሁን በዚህ ዘመን ላይ ሀገሪቱ ሀብታም (ቁሳዊ በሆነ) ሆና ማየት መገንዘብ እንዳንችልና ውለታዋን እንዳናውቀው ቢያደርገንም መታወቅ ያለበት ነገር ግን ይህች ቤተክርስቲያን ባትኖር ኖሮ እንደጠላቶቻችን ብዛትና እንደሚፈጽሙብን ሸር፣ ሴራ፣ ጥቃት፣ ጥረት ቢሆን ኖሮ ይህች ሀገርና ይሄ ሕዝብ ገና ድሮ ጠፍቶ ዛሬ ላይ ስም አጠራሩ የማይታወቅ ይሆን የነበረ መሆኑ ነው፡፡

ታዲያ ይሄ ልጅ እንዴትና ለምንስ ነው ይህችን የሀገር መሠረት የሆነችን ቤተክርስቲያን ጠምዶ ይዞ እያጠቃ ያለው? ያልን እንደሆነ በሦስት ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛውን ከላይ ያነሣሁት ባለጌነቱ ነው፡፡ የቀሩት ሁለቱ ደግሞ ለነገሩ ተያያዥ ስለሆኑ እንደ አንድ መቁጠርም ይቻላል፡፡ አንደኛው ማሰብ ማስተዋል መረዳት የማይችል ደንቆሮ ስለሆነ ሲሆን፡፡ ሌላኛው ደግሞ የዚህች ሀገር ጠላት ሀገራት ቅጥረኛ ባንዳ ስለሆነ ነው፡፡ ሁለቱን እንደ አንድ መቁጠር ይቻላል ያልኩት ባንዳና ቅጥረኛ የሚሆኑት ደናቁርቱ ማሰብ፣ ማስተዋል፣ መገንዘብ፣ መረዳት የማይችሉት እንጅ ብልሆች አስተዋዮች ሀገር ወዳዶች ባለመሆናቸው ነው፡፡

ታስታውሱ እንደሆን ይሄ ሰው ከሦስት ዓመታት በፊት እንግሊዝ ባዘጋጀችው ዓለማቀፋዊ የእስፖርት (የፍን፤ ሲነበብ ን ትጠብቃለች) ዝግጅት ላይ ከዓለም ሀገራት ከተጋበዙት የሥነጽሑፍ ሰዎች አንዱ ሆኖ ተጋብዞ ሔዶ ነበር፡፡ የተጋበዘው ካሉ የሥነ ጽሑፍ ሰዎቻችን የተሻለ ሆኖ ተገኝቶ እንዳልሆነ ሁላቹህም በግልጽ የምትረዱት ጉዳይ ይመስለኛል፡፡ ልጁ በወቅቱ ብቅ ብሎ መታየቱ ሌላ ጉዳይ ነው የአጠቃላይ የብቃትና የችሎታ የክንውን ጉዳይ ደግሞ ሌላ ጉዳይ ነው፡፡ እናም ስንት ከእሱ የተሻሉና ስንት ያበረከቱ እያሉ ወደ ስር እጃቸውን ሰደው እሱን አወጡትና ጋብዘው ወሰዱት፡፡ ለምን መሰላቹህ? ይሄንን ጉዳይ ገና እጀን ሳወጣ ምን ልል እንደምችል ገምቶ ነው መሰለኝ አቋርጦ ወጥቶ እዛው ባይሰማም ወደ እንግሊዝ ከመሔዱ ከቀናት በፊት እሱ ራሱ በነበረበት አንድ የመጽሐፍ መገምገሚያ መድረክ ላይ አንስቸው ነበር፡፡

በዚያ መድረክ ላይ ብየው የነበረው ነገር ምን መሰላቹህ፡- “በውቀቱ የተጋበዘበት ሰሞን ጋዜጣ ላይ ዐፄ ቴዎድሮስን እያብጠለጠለ እያዋረደ እያበሻቀጠ በተከታታይ ጽፎ ነበር፡፡ እናም አኔ ይሄንን በማስታወስ በውቀቱ የተጋበዘው ባንዳ ስለሆነ በሀገሩ ላይ ክህደት በመፈጸም ዐፄ ቴዎድሮስን በማብጠልጠል የእንግሊዝን ጥቅም ለማስጠበቅ ጥረት ስላደረገ ለዚህ ውለታው ነው የተጋበዘው እንጅ እሱን ለይተው ሊያወጡ የሚችሉበት ምን ጉዳይ አለ?” ብየ ስል ጥግ ላይ የነበሩ ደጋፊዎቹ እየተንጫጩ “ከመወያያ ርእስ ውጭ ነው! ያቁምልን!” በማለታቸውና በመረበሻቸው ስለ እሱ ተጨማሪ ነገር እንዳልናገር አደረጉኝ፡፡

እኔ ግን ከርእስ ውጭ ሆኘ አልነበረም ይሄንን የተናገርኩት፡፡ እየተገመገመ የነበረው “እሳት ወይ አበባ” የሚለው የሎሬት ጸጋዬ ገ/መድኅን የግጥም ሥራ ነበር፡፡ የመወያያ የጥናት ሐሳብ ያቀረበው ሰው “ቴዎድሮስ” የሚለውን የሎሬቱን ተውኔትም (ቲያትርም) አትቶ ስለነበር እኔም ዕድሉ ተሰጥቶኝ ሐሳቤን በማቀርብበት ጊዜ “የገባው ደራሲ የገባው ባለቅኔ የገባው ከያኔ አስተዋይና ልባም የሥነኪን ሰው እንዲህ የዐፄ ቴዎድሮስን ሰብእናና ማንነት በሚገባ ተረድቶ በድርሰት ሥራዎቹ አቅሙ የፈቀደለትን ያህል በዚህ መልኩ ይገልጸዋል እንደ በውቀቱ ያለ ደንቆሮ ባንዳና ቅጥረኛ ግን ዐፄ ቴዎድሮስን በፍጹም ሊረዳ አይችልም፡፡ ለዚህም ነው ያለ የሌለ እያወራ ዐፄ ቴዎድሮስን የተቻለውን ያህል ለማዋረድ ጥረት ያደረገው…” ስል ያቋረጡኝ፡፡ እናም የሱ ቢጤ የባንዳ ጥርቅም ስለሆኑ እንጅ ከርእስ ወጥቸ እንኳን አልነበረም እዚያ ድረስ እያወራሁ የነበርኩት ስለ ዐፄ ቴዎድሮስ ነበርና፡፡

እናም ይሄ ሰው ድንቁርናው ለባንዳነት አጋለጠው፡፡ ይሄው እንደምታዩትም የባንዳነት ሥራውን ተያይዞታል ወደፊትም ገና ብዙ ብዙ ያገለግላቸዋል፡፡ ኤምባሲዎች (የመንግሥት እንደራሴ መሥሪያ ቤቶች) የባሕል አታሸዎቻቸውን (ምድብ ሠራተኞቻቸውን) በመጠቀም ሀገራቸው በዚህ ሕዝብ ዕይታ እንዴት ዓይነት ገጽታ እንዳላትና በዚህ ሕዝብ ዘንድ ሀገራቸው የተበላሸ ገጽታ ካላትም የተለያየ መንገድ በመጠቀም ያንን የተበላሸ ገጽታ ለማስተካከል ጥረት ማድረግ፤ ለእነሱ በጎ አስተሳሰብ ላላቸው የሥነጽሑፍ ሰዎች ድጋፍ በማድረግ  ለገጽታ ግንባታና ከዚህም አልፈው የሀገራችንን ጥቅሞች በሚጻረሩ ጉዳዮች ላይ የሀገራቸውን ጥቅሞች ለማስጠበቅ መጠቀሚያ ማድረግ የመሳሰሉትን ሥራዎች ይሠራሉ፡፡ በውቀቱ የተመረጠው ለዚህ የበቃና የተመቸ ጥሩ ባንዳ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡

ባለፈው “በአይሁዶች መርዘኛ ጥርስ የገባች ሀገር ኢትዮጵያ!” በሚል ርእስ በጻፍኩት ጽሑፍ ላይ ከያኔያኖቻችንን እንዴት አድርገው አሳስተው ከሀገራቸው ጥቅም በተጻራሪ እንዴትና ለምን ዓላማ እንደሚጠቀሙባቸው በዝርዝር ለማስረዳት መሞከሬ ይታወሳል፡፡ ጽሑፉን ጎግል አድርጋቹህ እንድታዩት እየጠቆምኩ የልጁ በዚህ መልኩ መቀረጽ ከዚህ ማንነቱ አኳያ እንደሆነ ማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡ ለዚህም ነው ሁሉንም ነገሮች ሲመለከት የሚያይበት መነጽር የጥላቻ ከመሆኑ የተነሣ የሚታየው የሸማው ንጣት ሳይሆን ሸማው ላይ ያለችው ነቁጥ ጥላሽት የሆነው፡፡

በዚህች ምድር ላይ ፍጹም የሆነ ነገር የለም ካልንና “በውጉዝ ከመ አርዮስ” ቅኝት ልንተቸው የሚገባን ነገር በአብዛኛው ጥፋት የበዛበትን የሠራ አካል መሆን ካለበት በውቀቱ የሚጽፈው ሁሉ 95 ከመቶው ብላሽ ከንቱና ከላይ የገለጽኩት አስተውሎትና ሞያዊ አተያይ ያልተከተለ ነው፡፡ በሌላ ጊዜ “ከአሜን ባሻገር” በሚል ያሳተመውን መጽሐፉን በተመለከተ ትችቴን አቀርባለሁ፡፡ ከላይ ካልኩት አንጻር ሁሉንም ጅልነቱን ልንቀስ ብል፣ ጥልቅ ዕይታ ከማጣቱ የተነሣ የተሳሳተውን ሁሉ ልግለጥ ካልኩ ሌላ መጽሐፍ መጻፍ ሊሆንብኝ ነው፡፡ የቱን ትቸ የቱን እንደማነሣ አላውቅም፡፡

ሌላው ችግሬ ብዙዎቹ ሐሳቦቹ ቆዳቸው ብስል ውስጣቸው ጥሬ ከመሆናቸው የተነሣ እነዚህ የወረዱ አስተሳሰቦች ልተች ስል ለመተቸት የሚበቃ ክብደት የሌላቸው መሆናቸው ነው፡፡ እንዲህ ስል መጽሐፉ ጨርሶ እርባና የሌለው ነው ማለቴ አይደለም ጥቂትም ቢሆን ቁምነገር አይጠፋውም፡፡ ለምሳሌ ያ ነፈዝ ሸአቢያ በልብ ወለድ ድርሰቱ የነዛው የፋሽስት ጣሊያን የአኖሌና የጨለንቆ የጡት መቁረጥ ፈጠራን ፈጠራ መሆኑን ለማረጋገጥ የጻፈው በጣም ጥሩ ነው፡፡ እሱም ቢሆን ግን እኔ አሩሴ ሔጦሳ ላይ የቆመው የአኖሌ የጥፋት ሀውልት ከመመረቁ አስቀድሜና ከተመረቀም በኋላ በመጽሔቶችና ድረገጾች ላይ አከታትየ ከጻፍኩት የተለየ አልጻፈም እሱኑኑ ነው የቀዳው፡፡

ልዩነት ካለ እኔ በስም ያልጠቀስኳቸውን ባዕዳን ጸሐፍት በስም መጥቀሱ ነው፡፡ እኔ ብየ የነበረው ጉዳዩ ሐሰትና ፈጠራ መሆኑን ካተትኩ በኋላ “…ለኢትዮጵያ ጥላቻ ያላቸውና የራሳቸውን ፖለቲካዊ (እምነተ አሥተዳደራዊ) ጥቅም ለማስከበር በመጣር በጻፉ ባዕዳን ጸሐፍት እንኳን ይሄ የተባለው ነገር በአንዳቸውም መጽሐፍ ላይ ተጽፎ አልተገኘም፡፡ ካላቸው ዓላማና ጥላቻ የተነሣ ድርጊቱ ቢፈጸም ኖሮ ቢያንስ እነሱ ይጽፉት ነበር” ነው ብየ የነበረው፡፡ ብልጣብልጡ በውቀቱ ይህችን እንዳለች ወሰደና በሰጠሁት መንገድ ሔዶ የእነዚህን ጸሐፍት ስሞችን ከተተና ጻፋት፡፡ ይሄን በማድረጉ ግን አልከፋም ይህ የጥፋት ሐሳብ ሐሰት መሆኑ መናኘቱ ነውና ጥቅሜ ብየ የማስበው፡፡ እንዲህ የሚያደርጉኝን ሁሉ ልውቀስ ብል መጽሐፍ እያሳተሙ የቦጠቦጡኝን፣ አስፈቅደውም ሳያስፈቅዱም የመመረቂያ ወረቀታቸውን የሠሩትን ሁሉ ዘርዝሬ አልጨርሳቸውምና፡፡ በነገራችን ላይ በወቅቱ በዚህ ጉዳይ ላይ ከጻፍኳቸው ጽሑፎች በመጀመሪያው ጽሑፍ የታቻምናውን የኦሮሞ ተማሪዎች ዐመፅ ቀስቀሷል ብሎ ወያኔ ሁለቴ አስሮኝ ነበር ጉዳዩ እስካሁንም ገና ፍርድ ቤት እያንገላታኝ ያለ ጉዳይ ነው፡፡

በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ ያለ ሕዝብ ሁሉ አዋቂ አይሆንም ገለባም አለ፣ ድንጋይም አለ፣ እኩይም አለ፣ አረማዊም አለ፣ ምንደኛም አለ፣ ሆዳምም አለ፣ ጭራቅም አለ፣ ቀማኛም አለ፣ አታላይ ጮሌም አለ፣ እራስ ወዳድም አለ፣ አስመሳይም አለ፣ ጭንጋፉም አለ ወዘተረፈ. የሚገርማቹህ የተማረ ነው ከምትሉት ሰው ሁሉ ሳይቀር እነኝህን የሆነ አለ፡፡ በዚህም ምክንያት ነው ገለባውም ድንጋዩም እኩዩም አረማዊውም ምንደኛውም ሆዳሙም ጭራቁም ቀማኛውም አታላይ ጮሌውም እራስ ወዳዱም አስመሳዩም ጭንጋፉም ወዘተረፈውም የዚያን ማኅበረሰብ ሕዝብ የየድርሻቸውን ቢጤ ቢጤያቸውን በመውሰድ አድናቂ የማያጡት የሚያገኙት፡፡ ያለ ጥርጥር የበውቀቱ አድናቂዎች ደጋፊዎች እንደበውቀቱ የሚያስቡ የበውቀቱ አስተሳሰቦች የሚስማሟቸው ናቸው፡፡ እንደዚሁም ሁሉ የእነእንትና አድናቂዎችና ደጋፊዎችም እንትኖች ናቸው፡፡

ከዚህ አንጻር በውቀቱ ያገኘውን ያህል ትኩረት ማግኘቱ የሚደንቅ አይሆንም፡፡ በአንድ መንደር ያለ አዋኪ ዋልጌ በድርጊቶቹ የሰፈሩ መነጋገሪያ መሆኑ የማይቀር ነገር ነው፡፡ መልካም የሠሩትን የተለየ አስደናቂ ነገር አድርገው ካልተገኙ በስተቀር የሚያስታውሳቸው የለም፡፡ አዋኪው ዕለት በዕለት መነጋገሪያ ሆነ ማለት በሰፈርተኞቹ ልብ ውስጥ የክብር ቦታ አግኝቷል አለው ማለት አይደለም፡፡ ሰፈርተኞቹ ስለሱ የሚያወሩት ጎሽ የሚሉለትና የሚያበረታቱለትን ምግባር ስላገኙበት በአድናቆት ክብር ሰጥተውት ሳይሆን ትኩረት የሰጡት በእሱ ምክንያት በመታወካቸው፣ ሴት ልጆቻቸው ስለተደፈሩባቸው፣ ወንድ ልጆቻቸው ስለተጠቁባቸው፣ ንብረታቸው ስለተዘረፉባቸው፣ በእሱ ምክንያት ስለታመሱ ሰላም ስላጡ ነው ሳይወዱ በግድ ስለሱ የሚያወሩት፡፡

አደጋው እንግዲህ ይሄ ዱርየ በመላ ሰፈርተኛው ዘንድ መነጋገሪያ የሆነው በክፉ ሥራዎቹ መሆኑን መገንዘብ ተስኖት መነጋገሪያ መሆኑን እንደ ጀብድ ክብር የቆጠረው እንደሆነ ነው፡፡ እንዲህ ማሰቡ እሱ እስካለ ጊዜ ድረስ ያች ሰፈር ስትታመስ መኖሯ ነው ማለት ነው፡፡ ምንም ያድርግ ምን ለሱ ምኑም አይደለም፡፡ እሱ የሚፈልገው መነጋገሪያ መሆኑን ብቻ ነው፡፡ በውቀቱ ማለት እንዲህ ነው፡፡ ለዚህም ነው ማንን ምን ብሎ እንዴት መተቸት የማያውቀው ግብረገብ የጎደለው የሆነው፡፡

የገረመኝ ነገር “ምን ብየ ልጻፍና መነጋገሪያ ልሁን?” ብሎ መነሣቱ ነው፡፡ አንድ ጸሐፊ ነኝ የሚል ሰው እንዲህ ብሎ ከተነሣ ፀሐፊ አይደለም፡፡ ብስለትና ጥራት ያለውን ነገር ሊጽፍም አይችልም፡፡ በውቀቱ እንዲህ ብሎ በመነሣቱ በርካታ እጅግ ትዝብት ላይ የሚጥሉት ብላሽና ተራ የሆኑ ነገሮችን ሁሉ ለማለት ተገዷል፡፡ ሰው እንዴት “ምን ብየ መነጋገሪያ ልሁን?” ብሎ ይጽፋል? በዚህ አጋጣሚ ለበውቀቱ ማስተላለፍ የምፈልገው መልእክት ቢኖር ሳትዘገይ ወደ ጸበሉ ሒድ፡፡ እስክትበስል ድረስ ብታረጅም እንኳን ምንም ነገር አትጻፍ፡፡ ሀገርንና ሕዝብን ይቅርታ ጠይቅና ባንዳነትህን አውለልቀህ ጣል፡፡ ቢቸግርህም ከኅሊና ሰላም ጋር ያለ ድህነት ይሻላልና፡፡

እንዲሁም ለሱ ሽፋን እየሰጡ መነጋገሪያ እንዲሆን በአርዓያነት እንዲወሰድ ዕድል በሰጡት የብዙኃን መገናኛዎችም እጅግ ማዘኔን መግለጥ እወዳለሁ፡፡ እነዚህ ሰዎች የብዙኃን መገናኛ ከባድ ኃላፊነት የተሸከመና እጅግ ጥንቃቄ የሚፈልግ ተቋም መሆኑን ቢያስቡ መልካም ነው እላለሁ፡፡ የግል ፍላጎታቸውና ስሜታቸው ሌላ ጉዳይ ነው፡፡ ኃላፊነት ይዘው ሕዝብን ለማገልገል በተቀመጡበት ወንበር ላይ የግል ስሜትና ፍላጎታቸውን በማስተናገድ እንዲህ ዓይነት ስሕተት እየፈጸሙ በእሴቶቻችን በማንነታችን ላይ እያሴሩ ጠላቶቻችንን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ከሆነ ግን ይዋል ይደር እንጅ ከሕዝብና ከኅሊና ፍርድ ነጻ እንደማይሆኑ ሊያውቁት ይገባል፡፡ በውቀቱን በአርአያነት በሚያዩት፣ በሚያደንቁትና ደጋፊዎቹ በሆኑትም እጅግ ማፈሬን መግለጥ እወዳለሁ፡፡ በተለይ ተምረናል በሚሉት፡፡

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

amsalugkidan@gmail.com

በ18 ዓመት የተገኘው አስከሬን አሥራ ስምንት ዓመት እስራት አስቀጣ

$
0
0

የሰው ልጅ ገና ከጅምሩ ወደ ምድራዊ ህይወት ሲመጣ አብሮት የሚወለድ ሀብትና ንብረት እንደሌለው ሁሉም የሚያውቀው ሀቅ ነው:: ነገር ግን ከእለት ወደ እለት በሚያደርገው የስራ እንቅስቃሴ የሰዎች የኑሮ ደረጃ ዝቅተኛ፣መካከለኛ እና ከፍተኛ ሆኖ የሚታይበት ሁኔታ ግድ ሆኖ እናያለን::

በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኘው የህብረተሰብ ክፍል ደግሞ የእለት ጉርስ ለማግኘትና ቤተሰብ ለመርዳት ሲባል ወደ ጎረቤት ሀገር በመሔድ ያሰቡት ተሳክቶ ህይወታቸውን የሚቀይሩ እንዳሉ ሁሉ ባላሰቡት መልኩ ለችግር የሚጋለጡት በርካታ ናቸው:: እንደምሳሌ የምናነሳው ባሳለፍነው 2ዐዐ7 ዓ.ም በሀገራችን ዜጎች ላይ የደረሰው አሰቃቂ ግድያ ከህሊናችን የማይጠፋ ጠባሳ ነው:: ይህ ብቻ ሳይሆን ወደ ሀገራችን መለስ ስንል በከተማና በገጠር ተቀጥረው የሚሰሩ እህትና ወንድሞቻችን ላይም ቢሆን እንደ ውጭው ባይሆንም ከፍተኛ ጉዳት ሲደርስባቸው ይሰማል፣ይታያል::

ውድ አንባቢያን ከዚህ በመነሳት በአንድ የገጠር ቀበሌ ተቀጥሮ ስለ ነበረ አንድ ወጣት ልናስነብባችሁ ወደድን:: መልካም ንባብ

crime

በደስታው ሙላቴ | ፖሊስ እና እርምጃው ጋዜጣ

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን

ጎንደር ዞን ምስራቅ በለሳ ወረዳ አበየ ቀበሌ ልዩ ቦታው ቫርሳ ጎጥ በተባለ ቦታ ነበር ወጣት አሰፋ ተወልዶ ያደገው:: እንደ አጋጣሚ ሆኖ ወጣት አሰፋ ቤተሰቦቹ ዝቅተኛ ነዋሪ ስለነበሩ የቤተሰብ ሕይወት ለመለወጥ እራሱን ለማሻሻል በማሰብ በአካባቢያቸው ነዋሪ ከሆነ ከአቶ ብርሃኔ ፀጋው ጋር በመነጋገር በግብርና ስራ ይቀጠራል:: ወጣቱም አሰሪው በሚለው መሠረት የወደፊት ተስፋን በማንገብ በገጠር የሚሰሩ አረም፣ጉልጓሎ፣እርሻ፣እንጨት ለቀማ እና ከብቶችን በመጠበቅ ስራውን በትጋት መስራት ቀጠለ:: ገና ከጅምሩ ተቀጥሮ ሲገባ ሰርቶ ያፈራውን ገንዘብ ይዞ ወደ ወላጆቹ እንደሚመለስ ዕቅድ ነበረው::

አሰሪውም ይህን በሚገባ ያውቃል:: እናም ጊዜው ሲደርስ የሠራበትን የልቡን ዋጋ እንዲሰጠው ጥያቄ አቀረበ:: ጥያቄው ግን ምላሽ አላስገኘላትም:: አሰሪው ሌላ ተንኮል እንዲያስብ አደረገው እንጂ ከዛም ቀንና ሰዓት ጠብቆ ህይወቱ እንዲያልፍ ያደርግና በአካባቢው በመቅበር የእራሱን የተደላደለ ኑሮውን ይቀጥላል:: መቼም ከህብረተሰብ ጋር እየተኖረ የሚሰወር መረጃ አይኖርምና በሰዓቱ ወጣት አሰፋን ገሎ ወደ ግብዓተ መሬት ሲያስገባው የተመለከቱ ግለሰቦች ጥቂት አልነበሩም:: ቢሆንም ግን ገዳይ በአካባቢው ተፈሪ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ መረጃው ለፖሊስም ሆነ ለሟች ቤተሰብ ሊወጣ አልቻለም ነበር::

የወጣቱ ቤተሰቦች ልጁ ወደ ቤት የሚመጣበት ቀን ሲያልፍ ወደ ቦታው በመሄድ ወንድማቸው

የት እንዳለ ሲጠይቁ ልጁ ከእሱ ጋር እንደሌለ እና ከቤት መርቶ እንደሄደ ይነግራቸዋል:: የሟች ቤተሰብም በተፈጠረው ነገር በምሬት በማዘን ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ ይመጣ ይሆን በማለት በር በሩን ለወራት ብቻ ሳይሆን ለ18 ዓመት ማየት ጀመሩ:: አንድቀን ነገር ግን ወጣቱ እንኳን ሊመጣ የውኃ ሽታ ሆኖ ቀረባቸው:: ቤተሰቦቹ ጉዳዩን ህግ ማወቅ አለበት በማለት በለሳ ወረዳ ፖሊስ አመለከቱ:: ከአቶ ብረሃኔ ፀጋው በጉልበት ስራ ይሰራ እንደነበርና ለ18 ዓመት ቢጠብቁትም ሊመጣ እንዳልቻለ ቃላቸውን ሰጡ::

የወረዳው ፖሊስም የምርመራ ቡድኑን አዋቀረ:: ከሚመለከተው የፍትህ አካል የመፈተሻ ትዕዛዝ በማውጣት ከወረዳው ዐቃቤ ህግ ጋር በመሆን ድርጊቱ ወደተፈፀመበት አበየ ቀበሌ ልዩ ቦታው ቫርሳ ጎጥ ያመራሉ::

ከቦታው እንደደረሱ የአካባቢው ማህበረሰብ መረበሽ እንደሌለበት በመግለፅ በጥንቃቄ ቤቱን ሲፈትሹ ምንም አይነት መረጃ ሊገኝ አልቻለም:: ቢሆንም ግን ያለምንም ተስፋ መቁረጥ ከቤቱ ወጣ በማለት አካባቢውን መቃኘት ጀመሩ:: አሁንም ቢሆን የሚታይ ነገር አልነበረም:: በመጨረሻ እንደ አማራጭ የወሰዱት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በሚስጢር ውይይት አደረገ:: ነዋሪዎቹም የፖሊስ አጋር በመሆን ወጣቱን ገድሎ ከአካባቢው እንደቀበረው ጥቆማ ሰጡ::

ፖሊስም የፈለገው መረጃ ይህ ነበርና ለሁሉም

ሰው አካፋና ዶማ በመያዝ የተገኘውን መረጃ እውን ለማድረግ የወጣት አሰፋን አፅም ለማግኘት በተለያየ አቅጣጫ አስር ቦታ ላይ በመቆፈር ጀመሩ:: ቆፈሩ፣ቆፈሩ … ግን ሊገኝ አልቻለም:: ለ11ኛ ጊዜ ሲቆፈር እራሱንና ቤተሰቦቹን ለመርዳት ብሎ ከቤቱ የወጣውን ወጣት አሰፋ ስጋውን ሁሉ ለአፈርና ለምስጥ አስረክቦ እሱነቱን በማይገልፅ መንገድ አፈሩ ከጉድጓድ ሲወጣ ብቅ አለ::

በሰዓቱ አፅሙ መገኘቱ ጥሩ ቢሆንም ከሞተ በ18 ዓመቱ ያለምንም መረጃ ተዳፍኖ መቆየቱ ደግሞ ለምርመራ ቡድኑም ሆነ ለአካባቢው ማህበረሰብ መሪር ሀዘን ሆነባቸው:: ወጣት አሰፋ ተወልዶ ያደገበት አባየ ቀበሌ ቫርሳ ጎጥ የሚኖረው ማህበረሰብ መራር ሀዘኑን አዘነ::

ፖሊስም የገደለን መግደል ሳይሆን ወደ ህግ ማቅረብ ስለሆነ ዓላማው በሰዓቱ የነበሩ ግለሰቦችንና ሌሎች ማስረጃዎችን በማፈላለግ ለተወሰኑ ወራት ምርመራውን ቀጠለ:: የምርመራ መዝገቡን ካደረሰ በኋላ ተከሳሽ ባጠፋው ጥፋት የህግ ውሳኔ ያገኝ ዘንድ ለሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ይልካል::

የሰሜን ጎንደር ከፍተኛ ፍ/ቤት የምርመራ መዝገቡን ሲከታተል ከቆየ በኋላ ግለሰቡን ጥፋተኛ ሆኖ ስላገኘው የካቲት 17 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት 18 ዓመት ፅኑ እስራት የወሰነበት መሆኑን የምዕራብ በለሳ ወረዳ የምርመራ ክፍል ኃላፊ ም/ኢ/ር ደጉ ብርሃኑ ገልፀውልናል::

Health: በእንቅልፍ እጦት ይሰቃያሉ? –እንግዲህ ማር ይላሱ ያላሉ ዶክተሮች |የማር የጤና በረከቶችን ያንብቡ

$
0
0

Honey for health

ለማንኛውም በቤት ውስጥ በሚያገኟቸው አትክልትና ፍራፍሬ እንዴት ጤናዎን በቤትዎ በቀላሉ መንከባከብና ከበሽታ መከላከል እንደሚችሉ ለማወቅ የሚከተለውን ያንብቡ::

አልጋዎ ላይ ጋደም ብለው እንቅልፍ እምቢ ብሎዎት ሲገላበጡ እና አሁንም አሁንም በመንቃት ያለ እንቅልፍ ሌሊቱን አሳልፈውት ይሆናል።

ታዲያ ፈልገው ያጡትን እንቅልፍ ለማግኘት ምን አይነት ዘዴ ይጠቀማሉ?

ለምግብነት የሚጠቀሟቸው ምግቦች ለዚህ ፈውስ እንደሚሆኑ አስበው ሞክረውታል?

ለምግብነት ከሚጠቀሙት አንዱ የሆነው ማር ለሰውነት ከሚያስገኛቸው በርካታ ጠቀሜታዎች ባሻገር የእንቅልፍ እጦትን ለማስወገድም ይረዳል።

ጣፋጭ ነገሮችን በመኝታ ሰአት መጠቀም ጉዳት እንዳለው የህክምና ባለሙያዎቹ ይናገራሉ፤ ይሁን እንጅ ማር ከዚህ የተለየ እና ተፈጥሯዊ ጣዕም ባለቤት በመሆኑ በዚህ በኩል የሚመከር እንጅ የሚነቀፍ አይደለም።

በዚህ በኩል የማርን ሁለንተናዊ ጠቀሜታዎች አስመልክቶ መጻህፍትን የጻፉት ዶክተር ሮን ፌሰንደን፤ ማርን በገበታ ላይ በተለይም ደግሞ በእንቅልፍ ሰአት አካባቢ መጠቀም ከእንቅልፍ ጋር ለመታረቅ ሁነኛ መፍትሄ ነው።

ማር ለሰውነት ጠቃሚና ተፈጥሯዊ ይዘቱ አስፈላጊ በመሆኑም ሁሌም ቢሆን በየቀኑ መመገብ አዋጭ እንደሆነም ነው የሚናገሩት።

ከሁሉም በላይ ግን በመኝታ ሰአት አቅራቢያ

ማርን መጠቀም ጤናማ እና የተስተካከለ የእንቅልፍ ሰአት ለማግኘት ይረዳል ይላሉ፤ ከጣፋጭነቱ አንጻር ባይመስልም በመኝታ ሰአት ሰውነት በሚያደርጋቸው ሽግግሮች ወቅት የመታደስ ሂደቱን እንዲያገኝ ይረዳዋል።

ታዲያ ይህን የማር ጠቀሜታ ለማግኘት ካሰቡ ተፈጥሯዊውንና በአብዛኛው ከአርሶ አደሮች የሚገኘው ጥሬ እና ንጹህ ማር መጠቀሙ መልካም ነው፤ ከዚህ በታች ማር ያለውን የተወሰኑ ጠቀሜታዎች ይመልከቱ።

እንደ ዶክተር ፌሰንደን ገለጻ ከንጹህ ማር ግሉኮስ እና ከእፅዋት የሚገኘው ጣፋጭ ውህድ ( ፍሩክቶስ) በተስተካከለ መጠን ማግኘት ይቻላል። ይህ ደግሞ በእንቅልፍ ሰአት የጉበትን ስራ

የተስተካከለና ውጤታማ ያደርገዋል።

ንፁህ ማር በመኝታ ሰአት መጠቀምዎ ሌሊቱን ሙሉ ስራ የማይፈታው ጉበትዎ ለሰውነት ሃይልን የሚያከማቸውን ግላይኮጅንን በተሻለ መጠን እንዲያገኘው በማድረግ ሙሉ ሃይሉን ስራ ላይ እንዲያውል ይረዳዋል።

ታዲያ የወሰዱትን ማር በተመጠነ ውሃ ሲታጀብ ደግሞ በመኝታ ሰአት ከሚከሰቱ የጤና መዘዞች እና ድንገተኛ አደጋዎች ተጠበቁ ማለት ነው።

ማር በመኝታዎ ሰአት መጠቀምዎ በተለያዩ መንገዶች ተጠቃሚ ያደርግዎታል፤ ጉበትዎ 100 ግራም ግላይኮጅን ብቻ ይይዛል፤ ሰውነትዎ ደግሞ በቀን ውሎው በየሰአቱ 10 ግራም ያክል

ግላይኮጅን ይፈልጋል።

ታዲያ በመኝታ ሰአት ጉበትዎ ያከማቸው ግላይኮጅን ጥቅም ላይ ውሎ ያልቅና ተጨማሪ ይጠይቅበታል።

በመኝታ ሰአት የሚወሰድ ማር ትልቁ ጠቀሜታም ይኼው ነው፤ ለጉበት ግላይኮጅን ምንጭነት በበቂ ሁኔታ በማገልገሉ ምክንያት፤ ምሽት ላይ እስከ 2 የሻይ ማንኪያ ማርን መውሰድ ጉበት የሚፈልገውን የግላይኮጅን መጠን በበቂ ሁኔታ እንዲያገኝ ያስችለዋል።

ይህ ደግሞ በንጥረ ነገሩ እጥረት ሳቢያ በመኝታ ሰአት አዕምሮን ለከፍተኛ ጭንቀት እና ውጥረት ከመዳረግም ይታደገዋል።

ጤናማ ጉበት እንዲኖር በማድረጉና የእንቅልፍ እጦት የሚያስከትለውን የሜላቶኒንን ምርት በማስወገድ ሰላማዊ ሌሊትን እንዲያያሳልፉም ያግዛል።

ሌሊት ላይ የሚከሰቱ አላስፈላጊ የህመም ስሜቶችን በዚህ ወቅት በማስወገድ ሰውነት በእንቅልፍ ሰአት የሚያደርገውን ሽግግር ጤናማ እና የተስተካከለ ያደርገዋል።

ለየት ካለው የጤናማ እንቅልፍ ጠቀሜታው ባሻገርም ንፁህ ማር ባክቴሪያና ፈንገሶችን በመዋጋት እና በመከላከል ረገድ የተዋጣለት እንደሆነም ይነገርለታል። በዚህም የሰውነት መቆጣትን በእጅጉ ይከላከላል።

ከላይ ያሉትን ጨምሮ ያልተዘረዘሩትን በርካታ የጤና ጠቀሜታዎቹን ለማግኘት ንጹህ እና ያልተበረዘ ማር ይጠቀሙ።


Health: ቀረፋን የመመገብ 6 የጤና ጥቅሞች

$
0
0

cinmn
(በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር)
1. በአንቲ ኦክሲደንት የበለፀገ ነው
ቀረፋ በውስጡ ያዘው አንቲ ኦክሲደንት መጠን ቶሎ የማርጀትን ሁኔታ አንደሚያዘገይ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡
2. ለልብን ጤናማነት
ጥናቶች እንደሚሳዩት ከሆነ ቀረፋ ለልብ ሕመም ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሆኑታዎችን ይቀንሳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የኮሌስትሮል መጠን እንዳይጨምርም የመከላከል አቅም አለው፡፡
3. ስኳር ሕመም
ቀረፋ የስኳር ሕመምን የመከላከል አቅም ስለአለው በደም ውስጥ የሚገኘውን የስኳር መጠን ለመቀነስ ይረዳል፡፡
4. ካንሰርን ይከላከላል
አንቲ ኦክሲደንትን በውስጡ ያዘው ቀረፋ ለካንሰር ተጋላጭነታችንን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል፡፡
5. ኢንፌክሽንን ይከላከላል
የሰውነታችንን በሽታን የመከላከል አቅም የነበረ እንዲሆን ይረዳናል፡፡
6. ለጥርስ ጤናማነት እና ጥሩ የአፍ ጠረን
መጥፎ የአፍ ጠረን እንዳይኖረን እና በአፍ ውስጥ የሚገኙ ሕመሞችን በማድረግ ረገድ ከፍተኛ የሆነ ሚናን ይጫወታል፡፡
ጤና ይሰጥልኝ

በኢትዮጵያ የመኪናው አምራች ድርጅት ሃገሪቱን ባመሳት የውጭ ምንዛሪ እጥረት የተነሳ በምርት ላይ ችግር እንዳጋጠመው አስታወቀ

$
0
0

(ሪፖርተር) የቻይናው ሊፋን ግሩፕ ኩባንያ አካል የሆነው ሊፋን ሞተርስ፣ በአሁኑ ከቻይና እያስመጣ ከሚገጣጥማቸው ባሻገር ሙሉ ለሙሉ እዚሁ የሚመረቱ ተሽከርካሪዎችንና ሞተር ብስክሌቶችን ለመፍበረክ የነበረው ውጥን በውጭ ምንዛሪ እጦት ሳቢያ እየተጓተተበት እንደሚገኝ ገለጸ::

national bank of ethiopia

መንግሥት በተለይም ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት ላይ ያለበትን ችግር ቢቀርፍለት፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሞተር ብስክሌቶችን እዚሁ ለመገጣጠም እንደሚችል የሊፋን ሞተርስ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ማ ኩን (ማርክ) ለሪፖርተር አስታውቀዋል:: ማርክ እንዳብራሩት ከሆነ በኢትዮጵያ ሞተር ብስክሌት ለመፈብረክ የሚያስችል አቅም እንዳለው ቢገልጹም፣ አውቶሞቢሎችን ለመገጣጠም ግን በርካታ መሟላት ያለባቸው ነገሮች እንዳሉ ተናግረዋል:: ያልተቋረጠ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን ጨምሮ ሌሎች መሠረተ ልማቶች ግብዓቶች በአንድ ጊዜ ተሟልተው መቅረብ እንዳለባቸው አብራርተዋል:: ይሁንና እንዲህ ያሉ አቅርቦቶችን ያለምንም ችግር ሁሉንም በአንድ ጊዜ
ማግኘት ባለመቻሉ እንጂ መኪኖችን ከመገጣጠም ወደ ማምረቱ ለማቅናት ሊፋን ዝግጁ መሆኑን ይገልጻሉ::
የገጠመውን የውጭ ምንዛሪ እጥረት ለመቅረፍ አማራጭ አድርጎ የወሰደው የተገጣጠሙ መኪኖችን ለውጭ ገበያ ማቅረብ እንደሆነ የተናገሩት ማርክ፣ በተለይ ወደ ግብፅ ለመላክ የሚያስችሉትን ጥናቶች አጠናቆ ገበያውን ለመቀላቀል መቃረቡን አስታውቀዋል:: የመንግሥት ተቋማትን ጨምሮ ግለሰብ ደንበኞች መኪኖቹን እንደሚገዙት ያስታወቀው ሊፋን፣ በዓመት በአማካይ ከ500 እስከ 1,000 መኪኖችን ገጣጥሞ እየሸጠ እንደሚገኝ አስታውቋል:: ኩባንያው ዱከም ከተማ በሚገኘው የቻይና ኢስተርን ኢንዱስትሪ ዞን ውስጥ 20 ሺሕ ካሬ ሜትር የማምረቻ ቦታ በመግዛት ማምረት ከጀመረ ሰንበትበት ብሏል:: ከሆላንድ ካር ጋር በመኪና አካላት መለዋወጫ
አቅራቢነት አብሮ ሲሠራ ቆይቶ ከስምንት ዓመት በፊት ራሱን ችሎ ወደ መገጣጠሙ ሥራ የተቀላቀለው ሊፋን፣ ከዚያ በፊትም ወደ ኢትዮጵያ ገበያ የመጣው በሞተር ብስክሌት አቅራቢነት እንደነበር ይታወሳል::
ለገበያ ያቀረባቸውን ሁለት አዳዲስ ሞዴል መኪኖች ይፋ ማድረጉን በማስመልከት ሐሙስ፣ የካቲት 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በሸራተን ሆቴል ባካሄደው ዝግጅት ላይ የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ ሊፋን ኩባንያ እስካሁን ኢንቨስት ካደረገው በላይ ተጨማሪ ኢንቨስትመንት ማካሄድ እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል:: ኩባንያው ከስምንት ዓመት በፊት ኢንቨስት ያደረገው 1.5
ሚሊዮን ዶላር እንደነበርና በአሁኑ ወቅትም ስድስት ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስት ማድረጉን ዶ/ር ቴድሮስ አስታውሰው፣ ኩባንያው ሊያካሂድ ይገባቸዋል ያሏቸውን ሦስት አስተያየቶችንም ለኩባንያው ኃላፊዎች አቅርበዋል::
የመጀመሪያውና ኩባንያውም እየሠራበት እንደሚገኝ የገለጸው ወደ ውጭ የመላክ ተግባር ላይ እንዲሳተፍ የጠየቁበት ነው:: እንደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ ሊፋን በቀጣናው ያለውን ገበያ በአንክሮ ሊመለከተው ይገባል:: ለዚህ የሚያመች ዕድል አለ ብለው የጠቀሱትም፣ አገሪቱ የምትገኝበት ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ስትራቴጂካዊ በመሆኑ ነው::
ኢትዮጵያ በስምንት ሰዓት የአውሮፕላን በረራ ከ3.5 ቢሊዮን በላይ ሕዝቦችን ለማዳረስ የሚያስችላት አቀማመጥ ላይ የምትገኝ በመሆኗ፣
ለአገሪቱ ከሚያቀርበው ባሻገር ለቀጣናውና ከዚያም በላይ ላለው ገበያ የሚገጣጥማቸውን መኪኖች ማቅረብ እንደሚገባው ጠቁመዋል:: ዶ/ር ቴድሮስ ያቀረቡት ሌላኛው ሐሳብ ኩባንያው በአሁኑ ወቅት አሥር በመቶ እሴት በመጨመር
የሚያመርትበትን አሠራር ይበልጥ እንዲያዳብር፣
የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማምጣት የሚያስችለውን
ሚናውንም እንዲያሳድግ የኩባንያውን አመራሮች
እባካችሁ ብለዋል:: በመቀጠልም ‹‹ኢትዮጵያ
ለኢንቨስትመንትና ለኢንቨስተሮች ምቹ የመሆኗን
ዜና ለሌሎች አዳርሱ፣ ወሬውን አሰሙ፤›› በማለት
ጠይቀዋል::
ከዚህ በተጓዳኝም ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት
በማድረግ ትልቅ ድርሻ ከያዙት አገሮች መካከል
ቻይና ቀዳሚ መሆኗን፣ ቱርክ፣ ህንድ፣ ሳዑዲ
ዓረቢያ፣ ኔዘርላንድስና ዩናይትድ ኪንግደም በቅደም
ተከተላቸው ቻይናን በመከተል ከሁለተኛ እስከ
ስድስተኛ ያለውን ደረጃ የያዙ አገሮች መሆናቸውን
ዶ/ር ቴድሮስ አስታውቀዋል:: የቻይና መንግሥት ‹‹ጎ
ግሎባል›› በሚል ይፋ ያደረገውና አገሮችን ለመደገፍ
ባወጣው ፕሮግራምም በቻይና መንግሥት ቀዳሚ
ትኩረት ከተሰጣቸው አገሮች ውስጥ ኢትዮጵያ
ዋናዋ እንደሆነች አብራርተዋል::
የብረታ ብረትና ኢንዱስትሪና ኢንጂነሪንግ
ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ወርቅነህ
ደለለኝ፣ ኢትዮጵያ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በተለይም
በአውቶሞቢልና በኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች መስክ
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለመተካት ጭላንጭል
የሚታይበት ጊዜ ላይ እንደምትገኝ ተናግረዋል::
ይሁንና ይህ ሒደት ገና በእንጭጭ ደረጃ ላይ
ይገኛል ብለዋል::
ሊፋን ሞተርስ ኩባንያ፣ ኢትዮጵያን የአፍሪካ
ማዕከል በማድረግ ፋብሪካ ገንብቶ መንቀሳቀስ
ጀምሯል:: ምንም እንኳ በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ
እየጨመረ የመጣ ገበያ ቢኖረውም፣ የጠበቀውን
ያህል ሆኖ እንዳላገኘው ባለፈው ዓመት አስታውቆ
ነበር::
ባለፈው ዓመት ያስተዋወቀውን ሊፋን 530
ሞዴል መኪና ውስጥ አሥሩን ለገዥዎች ባስረከበበት
ወቅት፣ በኢትዮጵያ ሊፋን ሞተርስን በሚያካትተው
ያንግፋን ሞተርስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ
ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊዩ ጂያንግ እንዳስታወቁት፣
ሊፋን ሞተርስ በአፍሪካ ለሚኖረው የመኪና ገበያ
ኢትዮጵያን ቀዳሚ ምርጫው አድርጎ እየተንቀሳቀሰ
ቢሆንም በገበያ ችግር ምክንያት ኢትዮጵያን
የጠበቀውን ያህል ሆና አላገኛትም:: ገበያው ባገለገሉ
ተሽከርካሪዎች ጫና ውስጥ በመሆኑም ሳቢያ
አዳዲስ መኪኖችን የሚገጣጥሙ ኩባንያዎች ጫና
ውስጥ ወድቀዋል:: ይህንን መኪና በመጀመሪያ ዙር
እስከ አንድ ሺሕ የሚደርስ ብዛት ለአዲስ አበባ
የታክሲ ባለንብረቶች ማኅበር ለማቅረብ ስምምነት
ማድረጉን ምክትል ሥራ አስኪያጁ ለሪፖርተር
በሰጡት ማብራሪያ ገልጸዋል::
በየዓመቱ ከአንድ ሺሕ ያላነሱ መኪኖችን
የሚሸጠው ሊፋን፣ ገበያው ውስጥ ከሚታየው
ያገለገሉ መኪኖች ገበያ ባሻገር፣ በሎጂስቲክስ፣
በትራንስፖርትና በታክስ ወጪዎች ጫና እየደረሰበት
እንደሚገኝም አስታውቋል:: ገጣጣሚ ኩባንያዎች፣
ለገቢ ዕቃዎች ከ60 እስከ 70 በመቶ ያህል ግብር
የሚከፍሉ ቢሆንም፣ በተጨማሪ እሴት ታክስና
ኤክሳይስ ታክስ ምክንያት አስመጪዎች ከሚከፍሉት
እኩል እንደሚሆንና ይህም ለዘርፉ የተሰጠውን
ማበረታቻ እየቀነሰው መምጣቱን ይገልጻሉ::
በዕቅድ ደረጃ በዓመት አምስት ሺሕ
ተሽከርካሪዎችን እዚሁ ገጣጥሞ ለገበያ የማቅረብ
ሐሳብ እንዳለው ያስታወቀው ሊፋን፣ በሌሎች
አገሮች ውስጥ ያለው ዓመታዊ የመኪና ሽያጭ
መጠን ከመቶ ሺሕ በላይ በመሆኑ የኢትዮጵያ
እንቅስቃሴው ከሚጠብቀው በላይ ዝቅተኛ ሆኖ
እንዳገኘው ደጋግሞ ገልጿል::
ወጣት ቢንያም መንገሻ የሊፋን ሞተርስ የገበያና
የሽያጭ ኃላፊ ናቸው:: አቶ ቢንያም፣ የኩባንያው
የሽያጭ መጠን በየጊዜው እየጨመረ ቢመጣም፣
በአገር ውስጥ የሚታየው ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች
ከፍተኛ ተፈላጊነት ሳቢያ የአዲስ መኪኖች ገበያ ላይ
ችግር ይታያል ብለው ነበር::
ይሁንና በዚህ ዓመት ሁለት ተጨማሪ አዳዲስ
ሞዴሎችን እዚህ ገጣጥሞ ለገበያ ማቅረቡን ይፋ
አድርጓል:: ሊፋን X-50 እንዲሁም ሊፋን L-7
የተባሉትን ዘመናዊ አውቶሞቢሎች በ550 ሺሕ
ብር ተመሳሳይ ዋጋ ለገበያ ማቅረቡን ኩባንያው
አስታውቋል::

እስራኤል በኢትዮጵያ የቀሩ ቤተ-እስራኤላውያንን ወደ ሃገሯ ላለመውሰድ ወሰነች

$
0
0
(File Photo)

(File Photo)

ቤተ እስራኤላዊያኑ ወደተስፋይቱ ምድራቸው እስራኤል በያዝነው ዓመት የጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታናያሁ መንግስት በሚያደርገው አይሁዳዊያንን ወደምድራቸው የመመለስ ዘመቻ እንደሚወሰዱ ቃል ተገብቶላቸውና አስፈላጊውን ፎርማሊቲ በማሟላት ቀኑን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡

ባሳለፍነው ሰኞ ከጠቅላይ ሚኒስትሮ ቢሮ የወጣው መግለጫ ግን በኢትዮጵያ የሚገኙ ቤተ እስራኤላዊያኑን የሚያስደስት አይደለም፡፡የጠቅላይ ሚንስትሩን ውሳኔ ይፋ ያደረጉት ቃል አቀባዩ ኡዲ ፕራቨር በኢትዮጵያ የሚገኙትንና ወደእስራኤል ለመምጣት የሚጠባበቁትን በዚህ አመት እንደማንወስዳቸው ማሳወቅ እፈልጋለሁ፡፡ምናልባትም በእድሜ የገፉና የታመሙ 500 ያህል ቤተ እስራኤላዊያንን ከኢትዮጵያ ለማውጣት ሁኔታውን ግምት ውስጥ ልንከት እንችላለን››ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ በያዝነው ዓመት ብቻ ወደእስራኤል ለመሄድ ጉዞውን ይጠባበቁ የነበሩ ቤተ እስራኤላዊያን 9000 መሆናቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
የኔታናያሁ መንግስት ውሳኔን በመቃወም ሁለት የሊኩድ ፓርቲ አመራሮችና የሴኔቱ አባላት ተቃውሟቸውን በማሰማት ቤተእስራኤላዊያኑ ወደ ተስፋይቱ ምድራቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ ጠይቀዋል ይህ ካልተደረገም በሴኔቱ ድምጻችንን ለጥምረት ፓርቲ በመስጠት ሊኩድን ዋጋ እናስከፍለዋለን በማለት ዝተዋል፡፡
በሴኔቱ የኔታናያሁ ሊኩድ ፓርቲ 61-59 በሆነ ጠባብ የወንበር ብልጫ እየመራ የሚገኝ ሲሆን ሁለቱ አባላት እንደተናገሩት የሚያደርጉም ከሆነ ለሊኩድ ነገሮች ጥሩ እንደማይሆኑ ተነግሯል፡፡
በ1980ዎቹ እስራኤል በ10.000 የሚቆጠሩ ቤተ እስራኤላዊያንን ከኢትዮጵያ መውሰዷ አይዘነጋም፡፡ከዚህ ጉዞ ውጪ ሆነው የቀሩት ደግሞ በያዝነው ዓመት ለመጨረሻ ጊዜ እንደሚወሰዱ ቃል ተገብቶላቸው በተስፋ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡
ምንጭ ኢየሩሳሌም ፖስት

“የአማራን ሕዝብ ትጥቅ አስፈቱ” አባይ ወልዱ –ኦህዴድ ሳያገግም፤ ብአዴን ሊደገም?

$
0
0

demeke-muktar-e1457323281819-948x408

ኢትዮጵያን በተገንጣይ ስም የሚመራው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር – ህወሃት፣ የገጠመው ቀውስ እየተለጠጠበት ነው። ኦህዴድ አደረጃጀቱ ሊጠገን በማይችልበት …

በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

ኢትዮጵያን በተገንጣይ ስም የሚመራው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር – ህወሃት፣ የገጠመው ቀውስ እየተለጠጠበት ነው። ኦህዴድ አደረጃጀቱ ሊጠገን በማይችልበት ሁኔታ ተናግቶበታል። ይኽው ወረርሽኝ ወደ ሌሎች ገባር ድርጅቶች መስፋፋቱ የማይቀር ቢሆንም ብአዴን ውስጥ ቀውስ ስለመነሳቱ መረጃዎች ከቀድሞው በላይ ጎልተው እየወጡ ነው።

በ1997 ምርጫ ኢህአዴግን ከውድቀት ጉድጓድ ያወጣው ኦህዴድ፣ ህወሃት በአንጃ ተቧድኖ ሲባላ የመለስን ወገኖች የታደገው ብአዴን አሁን ለህወሃት መከራ ሆነውበታል። አጋር የሚባሉት ድርጅቶችም ውስጥ ተመሳሳይ ችግሮች እንዳሉ የራሱ የህወሃት መገናኛዎች እየመሰከሩ ነው።

የችግሩ አሳሳቢነት ቀላል ባለመሆኑ ኦሮሚያና ጋምቤላ ተሸንሽነው “በጊዚያዊ ወታደራዊ አስተዳደር” ሥር ወድቀዋል። ይህንኑ እውነት አሁንም የራሱ የህወሃት ልሳኖች አምነው ይፋ አድርገውታል። አንድ ወጥ አገር በነጻ አውጪ ቡድን፣ በፌዴራል መዋቅር፣ በጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር፣ በሱዳን ሚሊሺያ፣ ወዘተ የተዘበራረቀ አመራር ላይ መውደቋ የወደፊቱን የመለስ “ራዕይ” አመላካች ስለመሆኑ አስተያየት እየተሰጠ ነው።

ነገሮች እንደዚህ በጦዙበት ወቅት “የታላቋ ትግራይ” ድንበር ሙሉ የሁመራን ለም ምድር የሚያጠቃልል፣ ጠገዴንና ወልቃይትን የሚውጥ፣ እንዲሁም ኤርትራ ግዛት ጠልቆ የሚገባ መሆኑ ቦታና ስም ተዘርዝሮ ይፋ መሆን ጀምሯል። በሌላ ጎኑ ኦህዴድ ውስጥ “ህዝብ ለምን አመጸ፣ የጸጥታ ሃይሉ እንዴት ከጃችን ወጣ? የታች መዋቅሩ እንዴት ፈረሰ? ድርጅታዊ ሠንሰለቱ እንዴት ተበጠሰ? ታማኝነትና ጠባብነት …” ማለቂያ የሌለው ግምገማ  እየተካሄደ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ  የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚና የኦህዴድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳባ ደበሌ፣ የኦሕዴድ ሥራ አስፈጻሚና የኦሮሚያ ክልል አስተዳደርና ፀጥታ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ኩቹ ለጊዜው ከተመደቡበት ያገለጋይነት ሹመት ተነስትው ቀለበት ውስጥ እንዳሉ ተሰምቷል። ሹም ሸሩ ቀጣይ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።

በህወሃት አደረጃጀት “ጸጥታ” የሚለው ሹመት የስለላው ምሶሶ ዘርፍ ነው። የኦህዴድ የፀጥታ ሃላፊ ተነሱ ማለት ስለላው ተናግቷል ወይም እንደ ቀድሞ መረጃ አያገኝም ማለት ነው። ይህ የሚሆነው ደግሞ አንድ ለአምስት የሚባለው የስለላ መዋቅር ውሃ በለቶታል ማለት ነው። አሁን እንደ አዲስ ቢደራጅ የሚተገበረው ቀድሞ ታች ባሉት አመራሮችና ካድሬዎች ላይ በመሆኑ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም በማለት ስለ አደረጃጀቱና ስለ ወቅቱ ግለት የሚያውቁ እየገለጹ ነው።

በየቀበሌው ድምጻቸውን ያሰሙ ወገኖች ተገልለዋል፤ በሺህ የሚቆጠሩ ታስረዋል። የተሰደዱ፣ ቀያቸውን ጥለው የኮበለሉ፣ ዱር ያሉ፣ ከዚህም በላይ ሃዘን ያደቀቃቸውና የሚጠዘጥዛቸው ቤተሰቦች፣ ዘመዶች፣ የወንዝ ልጆች፣ ኦሮሞዎች፣ ኢትዮጵያውያን አዝነዋል። የቂም ቋጠሯቸው ጠብቋል። የፈሰሰው ደም ከሚያንዘፈዝፋቸው  ክፍሎች መካከል የታችኛው ካድሬና አመራር በግንባር ቀደምትነት የሚሰለፍ ነው። በዚህ መነሻ ህወሃት እነዚሁ ዜጎች ላይ ታዛዥ ሃላፊ ቀይሮ እንደ ቀድሞው ልፈንጭ፣ ለጋልብ፣ ልፍለጥ፣ ልቁረጥ ቢል አይሳካለትም ሲሉ እነዚሁ ክፍሎች ያብራራሉ።

ምሳሌ ሲያነሱ አርሲ የሆነውን ይጠቀሳሉ። የኦሮምያ ፈጥኖ ደራሽ አባል ወገኖቹን ሊገድል የመጣውን የአጋዚ ቅጥረኞችን መሳሪያ አዙሮ ረሸነ። አስራ አንዱን ሲገድል አንዱን አንገቱ ላይ ቆሞ ነው እያቀራራ ጥይት ያዘነበበት። ተቺዎች እንደሚሉት የዚህ ፖሊስ ተግባር መጪውን የሚያመላክት ነው። ህወሃት ብቻ ሳይሆን ሌሎችም በብሄራቸው ላይ የሚፈጸም ግፍ ያማቸዋል። በዝርፊያ የበሰበሱትን ሳይጨምር።

የበታቹ ካድሬ የዝርፊያ ጉዳይ አያሳስበውም። አብዛኛው ደግሞ ይህ የህብረተሰብ ከፍል ነው። ባንድ ግምገማ ላይ አንድ የህወሃት ሰው ስለ ሙስና አንስተው ሲገመግሙ አንድ ከንቲባ ተነስተው “እርስዎ ቤተሰቦችዎን እየላኩ መሬት ይወስዱ አልነበረም” ሲል ሞግተዋቸው እንደነበር የሚያስታውሱ “አሁን የበላዩ የበታቹን ሲገመግም አዳራሹ በሽሙጥ ይሞላል፤ ሌላውን ለመወንጀል ንጹህ ጀርባ ያላቸው ስለሌሉ የሚታየው ሁሉ ከበሰበሰ እንቁላል ጫጩት የመከጀል ያህል ነው” በሚል ህወሃት ብስባሽ ላይ ሆኖ እንደሚወራጭ ያስረዳሉ።

በኦሮሚያ መዋቅር ፈርሶ ሽማግሌዎች መሬት ለተወሰደባቸው ሲያከፋፈሉ ነበር። አጋርፋ አካባቢ ይህ ተፈጽሟል። ይህንን ህዝብ መልሶ ማደራጀት ጅልነት እንደሆነ የሚጠቁሙ ክፍሎች ህወሃት በቅጡ አስቦና መክሮ ወደ ትክክለኛው መፍትሄ ሊመጣ እንደሚገባው ይመክራሉ። አያይዘውም በሌሎች የህብረተሰብ ከፍሎች ላይ የሚፈጸመው ግፍ አድሮም ቢሆን ዋጋ ስለሚያስከፍል በስማቸው የሚፈጸመው ወንጀል ይቆም ዘንድ የትግራይ ንጹሃን ድምጻቸውን ሊያሰሙ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

አማራ ክልልም ቢሆን የተሳከረ ችግር ስለ መኖሩ ህወሃት የማይክድበት ደረጃ ላይ ነው። ባለፈው ሳምንት የትግራይ ክልል ፐሬዚዳንት የአማራ ክልል አስተዳዳሪን ውይይት ላይ “አማራን ትጥቅ አስፈታ” የሚል ትዕዛዝ አዘል ንግግር ሲናግሩ “የምን ትጥቅ ነው የማስፈታው? አንተ ግምጃ ቤት ከፍትህ ለትግራይ ህዝብ መሳሪያ እያደልክ” የሚል መልስ እንደሰጡ በተለይ ለጎልጉል መረጃ የላኩ አስረድተዋል።

የወልቃይትን ጉዳይ ከህወሃት ፍላጎት አንጻር የብአዴን ስራ አስፈጻሚ እንዲቀበልን አቋም እንዲይዝ ትዕዛዝ ቢሰጥም “በቀጥታ ከህዝብ ጋር የምንገናኘው እኛ ነን፤ ይህንን አንቀበልም፤ ልታስፈጁን ነው?” የሚል ምላሽ ከበታች ካድሬዎች ተሰንዝሯል። እንደ ዜናው አቀባዮች ከሆነ ብአዴን ውስጥ ኦህዴድ ላይ የደረሰው የበታች አመራር መንሸራተት እየታየ ነው።

የብአዴን ማዕከላዊ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርጓል፡፡ በመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ፣ ከቅማንት ማኅበረሰብ ማንነት ጋር በተያያዘ የተከሰተውን ችግርና የግጭት አፈታት ተግባራትን፣ በአማራና በትግራይ ክልሎች በፀገዴ ወረዳዎች የተከሰተውን ችግርና በሁለቱ ክልሎች የተደረገውን ምክክር፣ በክልሉ በድርቅ የተጠቁ 2.3 ሚሊዮን ዜጎችን በተመለከተና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ለሦስት ቀናት መክሯል ሲል ሪፖርተር ዛሬ ዘግቧዋል።

ሰሞኑን በሁለት የኦህዴድ ከፍተኛ አመራሮች ላይ በተወሰደው እርምጃ የተጀመረው ኦህዴድን የማጽዳት ተግባር በርካታ የአመራሮች ላይ ሰይፉን እንደሚያሳርፍ ከወዲሁ የሚያመላክቱ በርካታ መረጃዎች አሉ፡፡ ከሁለት ወር ተኩል በፊት ጎልጉል የኦህዴድ ህወሃት/ኢህአዴግን መክዳት አስመልክቶ በጻፈው የዜና ዘገባ ላይ እስካሁን የተሠራው ጥርነፋም ሆነ የህወሃት የበላይነት የተፈለገውን ውጤት ሳያመጣ ቀርቶ ኦሮሚያን ለከፋ ችግር እንደዳረጋት ተጠቅሶ ነበር፡፡

ይህ የኦህዴድ ችግር ገና መስመር ሳይዝ አሁን ደግሞ ህወሃት ወደ ብአዴን ላይ ለመዞር ማሰቡና “ትጥቅ” ለማስፈታት የሚያደርገው እንቅስቃሴ ጉዞውን ከድጡ ወደ ማጡ ያደርገዋል የሚለው አስተያየት የበረከተ ነው፡፡ ከሁሉ በላይ ኦህዴድና ብአዴን አብረው ህወሃትን ብቻውን ቢያስቀሩት የፖለቲካውን አሰላለፍም ሆነ የአገሪቱን የወደፊት አቅጣጫ ባልታሰበ መልኩ ይቀይረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡

አርቲስት ኤፍሬም ታምሩ ተከሰሰ

$
0
0

ephrem Tamiru 2015
አርቲስት ኤፍሬም ታምሩ “ለቀይ ዳማ ” ሙዚቃ የዜማ ደራሲ ክፍያ ሳይከፍል ሙዚቃውን ለህዝብ አቅርቦታል በሚል ክስ ተመሰረተበት።
ከሳሽ ወይዘሮ ቤተልሄም ማስረሻ የሙዚቃው ዜማ ደራሲ ልጅ ሲሆኑ፥ አርቲስት ኤፍሬም ታምሩለፈጠራው ስራ እና ህግ በመጣሱ 170 ሺህ ብር እንዲከፍል ክስ አቅርበውበታል።
የከሳሽ ወላጅ አባት አርቲስት ማስረሻ ሽፈራው፥ በ1977 ዓ.ም ታትሞ በወጣው የሙዚቃ አልበም ”ቀይ ዳማ” ወይም “የድንገት እንግዳ” ለተባለው ሙዚቃ ደራሲ መሆናቸውን የክስ መዝገቡ ያስረዳል።
ከሳሽ አባቴ በህይወት ባይኖርም ይህ መብቱ ግን በውርስ ለእኔ ተላልፎ እያለ ተከሳሽ የቅጅ እና ተዛማች መብቶችን ሳያከብር ከፈቃዴ እና ከእውቅናዬ ውጭ የህግ ጥበቃ የተደረገለትን የሙዚቃ ስራ እንደገና በመዝፈን በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን እንዲለቀቅ አድርጓል በማለት ነው ክሳቸውን ያቀረቡት።
ከዚህ ባለፈም አስቀድሞ የሰራቸውን ስራዎች በድጋሚ እንደሚሰራ በማስታወቅ እና ዘፈኑን ለማስታወቂያ ስራነት በማዋል ከፍተኛ ጥቅም አግኝቶበታል በማለት ከሳሽ፥ ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 6ኛ ፍትሃ ብሄር ችሎት ክሳቸውን አቅርበዋል።
በመሆኑም ተከሳሽ ለዜማ ደራሲው ፍቃዱን አግኝቶ ቢሆን ኖሮ ሊከፍለው የሚገባውን 30 ሺህ ብር እንዲሁም የከሳሽን ፈቃድ ሳያገኝ በህግ ጥበቃ የተደረገለትን መብት በመጣስ ለደረሰብኝ የሞራል ጉዳት አርቲስቱ 140 ሺህ ብር ይክፈለኝ ሲሉም ለፍርድ ቤቱ የዳኝነት ጥያቄ አቅርበዋል።
በወይዘሮ ቤተልሄም ማስረሻ በኩል ክስ የተመሰረተበት አርቲስት ኤፍሬም ታምሩ፥ ከሳሽ ከሟች አባታቸው አዕምሯዊ ንብረቱ በውርስ የተላለፈ መሆኑን የሚያሳይ ማስረጃ የላቸውም በማለት የመጀመሪያ መቃወሚያውን አቅርቧል።
አርቲስቱ ከሳሽ መብታቸውን መጠየቅ የነበረባቸው ወላጅ አባታቸው ካለፉ እስከ ሶስት አመት ባለው ጊዜ ቢሆንም፥ ክሱን ያቀረቡት ከ13 አመት ከ6 ወር በኋላ መሆኑ ግን ክስ የማቅረብ መብታቸው በይርጋ የታገደ ነው በማለት መቃወሚያውን ለችሎቱ አቅርቧል።
በተጨማሪም ከሳሽ ክስ ለማቅረብ የተረጋገጠ መብትና ጥቅም (vested interest) የላቸውም በማለትም ነው አርቲስቱ መቃወሚያውን ያቀረበው።
ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው ፍርድ ቤቱ፥ መዝገቡን መርምሮ በመጀመሪያ ደረጃ የክስ መቃወሚያ ላይ ብይን ለመስጠት ለመጋቢት 27 ቀን 2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል።
***
ምንጭ፣ ኤፍ ቢ ሲ
የካቲት 29 /2008ዓ.ም
አዲስአበባ

ጥቂት ስለ ቃሊቲ የሴቶች መቆያ እና ማረሚያ ቤት –በማሕሌት ፋንታሁን

$
0
0

የማይቻል ነገር እንደሌለ በተግባር ለማየት ከሚያስችሉ ሁኔታዎች አንዱ የእስር ቤት ሕይወት ነው። እስር ቤት እንገባለን የሚል እሳቤ በአይምሯችን ውስጥ ስለማይኖር በአብዛኛው ከተለመደው የኑሮ ዑደት (መወለድ፣ ማደግ፣ መማር፣ መሥራት፣ ማግባት፣ መውለድ፣ ማደርጀት እና መሞት) እና ተያያዥ ጉዳዮች ተነስተን ነው የግል አቋማችንን የምንቀርፀው። “ከሰው ጋር መተኛት አልወድም/አልችልም፤ እንቅልፍ አይወስደኝም”፣”ስፕሪስ ሳልጠጣ መዋል አልችልም”፣ “የቀዘቀዘ ምግብ አልወድም”፣ “ሲጃራ ሳላጨስ መኖር አልችልም”፣ “በቀን ቢያንስ ሁለት ፊልሞችን ካላየሁ አልደሰትም”፣ “እከሊትን/እከሌን ሳላይ መዋል አልችልም”፣ “ጨለምለም ካላለ ወደ ቤት መግባት አልወድም”፣ “መብራት ካልጠፋ እንቅልፍ አይወስደኝም”እና የመሳሰሉ የማይለወጡ የሚመስሉን አቋሞቻችን ፈተና ውስጥ የሚወድቁት የእስር ሕይወትን ‹ሀ› ብለን ስንጀምር ነው። ብዙ አልችልም ብዬ የማስባቸውን ነገሮችን ችዬ ስለወጣሁበት ስለ ቃሊቲ የሴት እስረኞች ግቢ ጥቂት ልበላችሁ።

Compiled

በቃሊቲ እስር ቤት ግቢ ውስጥ ከሚገኙት8 ዞኖች ሁለቱ የሴት እስረኞች የሚኖሩበት ነው። በአንደኛው ዞን በቀጠሮ ላይ የሚገኙ ሴቶች በሌላኛው ደግሞ የተፈረደባቸው ሴቶች ይኖሩበታል። ልዩ ጥበቃ ወይም የቅጣት ቤት የሚባሉ ቤቶች አሉ። ወይም በተፈለገበት ሰዓት ይሠራሉ። ለምሳሌ ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ከማንም እስረኛ ጋር እንዳትገናኝ 5ት ሰው ብቻ የሚኖርበት የቅጣት ቤት ውስጥ ነበር የምትኖረው። ISISን በመቃወም ከተጠራው ሰልፍ ጋር በተያያዘ ሚያዚያ ወር 2007 የታሰሩ ሴቶች ከሌሎች ጋር እንዳይገናኙ ለብቻቸው በተሠራላቸው ቤት ይኖሩ ነበር።

በቀጠሮ ዞን ደግሞ 5 ቤቶች ያሉ ሲሆን በፍርደኛ ግቢ 6 ቤቶች አሉ።አንድ ቤት ውስጥ ከ 40 እስከ 120 እስረኞች ይኖራሉ። ቀጠሮ ግቢ ከአንዲት አነስተኛ ሱቅ በስተቀር ሌላ ምንም ስለሌለ የተለያዩ ነገሮችን ለመገበያየት እና ፀጉር ቤት ለመጠቀም ፍርደኛ ግቢ መሄድ ግድ ይላል። ቤተሰብ መጠየቂያ ቦታው የፍርደኛ ግቢን አቋርጦ የሚገኝ ቦታ በመሆኑ፤ በቤተሰብ መጠየቂያ ሰዓቶች (ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2:30 እስከ 6:00 ከሰዓት ከ7:30 እስከ 10:00 እንዲሁም ቅዳሜና እሁድ ጠዋት ከ2:30 እስከ 6:00)፤ ቀጠሮ ክልል የሚገኙ እስረኞች ከፍርደኛ ክልል ማግኘት የሚፈልጉትን ነገር ማግኘት ይችላሉ። በቀጠሮ እና ፍርደኛ ክልል መሐል 200 ሜትር ገደማ ርቀት ያለው ሲሆን በየግቢዎቹ በር እና ማማዎች ላይ ጠባቂ ፓሊሶች አሉ። ዞኖቹ (ቤቶቹ) ከአስተዳደር ጀምሮ በእስረኞች በተመረጡ የእስረኛ ኮሚቴዎች ይመራል። በየቤቱ ለሊት የሚደረግ ጥበቃ አለ። ሮንድ ይባላል። እያንዳንዷ እስረኛ ተራዋ በደረሰ ቀን ለሁለት ሰዓት ከሌላ አንድ እስረኛው ጋር ይጠብቃል። ከለሊቱ 5:00 ሰዓት እስከ 7:00 እና ከ7:00 ሰዓት እስከ 9:00 ሮንድ ተረኞች የሚጠብቁበት ሰዓት ነው። የእስረኞች ቆጠራ በቀን ሁለቴ ይካሄዳል። የጠዋት ገቢ ፓሊሶች ከጠዋቱ12:00 ላይ፤ 11:30 ላይ ደግሞ የማታ ገቢ ፓሊሶች ቆጥረው ይረከባሉ።

የስድስት ሰዓት ተጠያቂዎች

ከላይ የጠቀስኳቸው የእስረኛ”መብቶች” እኛ የስድስት ሰዓት ተጠያቂዎች ጋር ሲደርስ ቅንጦት ይሆናሉ። እንኳን በውናችን በሕልማችንም አናስበውም።”ይቺም ቂጥ ሆና ለሁለት ተከፈለች” ዓይነት ነገር ነው። ያም መብት ተብሎ ተሸራርፎ ሲሰጠን እና ስንከለከል “All animals are equal but some are more equal” የሚለው አባባል ትዝ ይለኛል። የስድስት ሰዓት ተጠያቂዎች ማለት በሽብር ወይም በአመፅ ማነሳሳት የሚል ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸውን በቀጠሮ ክልል ሆነው የሚከታተሉ ወይም ተፈርዶባቸው ፍርደኛ ክልል ያሉ ሴቶች ማለት ናቸው። ስያሜው የመጣው ከቤተሰብ ጋር ከምንገናኝበት ሰዓት የተወሰደ ነው። የምንጠየቀው 6 ሰዓት ላይ ብቻ ሲሆን እኔ በቆየሁባቸው ጊዜያት ከ10 ደቂቃ እስከ 30 ደቂቃ ለሚሆን ቅፅበት ነበር። የመጀመሪያዎቹ የስድስት ሰዓት ተጠያቂዎች ለ5 ደቂቃ ብቻ ይገናኙ እነደነበር ሰምቻለሁ። ከዚህ በተጨማሪም የምንጠየቀው በቅርብ ቤተሰቦች ብቻ ነው። ያለንበት ዞንም ሆነ ቤት በኮሚቴነት መመረጥም መምረጥም አንችልም። ሮንድ ጥበቃ እኛን አያካትትም። ፍርደኛ ግቢ ሄዶ መገበያየት ይናፍቀናል። ቢበዛ የ6 ሰዓት ተጠያቂ ያልሆነ(ኖርማል) እስረኛ እንድንልክ ቢፈቀድልን ነው። ሆኖም ግን አስጠጪ እስረኞች ሰበብ ፈልገው የሚላኩትን ኖርማል እስረኞች ለአሸባሪ ይላላካሉ የሚል ክስ ስለሚያቀርቡባቸው፤ የሚላክልን ማግኘት እስቸጋሪ ነው።

ክሊኒክ እና ፀጉር ቤት ለመሄድ ስንፈልግ ለብቻችን አጃቢ ተመድቦልን ነው። የምትመደብልን አጃቢ ፀጉር ቤት ውስጥ ገብታ ተሰርተን እስክንጨርስ ጠብቃ ይዛን ትመለሳለች። ይሄ ሲገርመን የሆነ ጊዜ ላይ ፓሊሶች የሚሰሩበት ፀጉር ቤት እንድንጠቀም መመሪያ ተላለፈ። ይህ መመሪያ ከተላለፈ በኋላ የሆነ ቀን ጋዜጠኛ ርእዮት አለሙ ፀጉር ቤት ለመሄድ ጠይቃ፤ አጃቢዋ እየወሰደቻት የተላለፈውን መመሪያ ስትነግራት “እኔ እስረኛ ነኝ። ለምንድነው የፓሊስ ፀጉር ቤት የምሰራው? ይቀራል እንጂ!” ብላ ፀጉሯን መሠራቱን ትታ ተመለሰች። እስክትወጣ ድረስም በአቋሟ እንደፀናች ነበር። ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬም የሚደርስብንን መገለል በመቃወም ፀጉሯን በመላጨት መልዕክት አስተላልፋአለች።

ስድስት ሰዓት ላይ ቤተሰብ ልንጠይቅ ስንወጣ እና ስንገባ በአጃቢ ነው። ቤተሰብ ስናወራም የምናወራውን የሚሰሙ ከኛም ከቤተሰባችንም በኩል ፓሊሶች ይቆማሉ። ቤተሰብ ለማገናኘት ከሚወስዱን አጃቢ ፓሊሶች በማይሰሙት ቋንቋ ከቤተሰብ ጋር ማውራት አይቻልም። ከግቢያችን ስንወጣም ሆነ ወደ ግቢያችን ስንገባ ከኖርማል እስረኞች በተለየ ብርበራ ይካሄድብናል። ቤተሰብ ልንገናኝ ስንሄድ ፍርደኛ ክልል ያሉ የሚያቁን እስረኞችን ጋር በዓይን እንኳን ሰላም መባባል አይቻልም። እነሱም ሰላም ካሉን የተለያየ ቅጣት ይደርስባቸዋል። እኛ በምናልፍበት ሰዓት ከቤት እንዳይወጡ መከልከል፣ በካቴና መታሰር እና በአጃቢ መንቀሳቀስ የተለመዱት ዓይነት ቅጣቶች ናቸው። ባስ ሲልም እስከ አመክሮ መከልከል ይደርሳል። ማንኛውም ዓይነት ጽሑፍ የተጻፈባቸው ማስታወሻ ደብተሮቻችን በፍተሻ ወቅት ይወሰዳሉ። ፍተሻዎች እኛ ላይ እና ከኛ ጋር ይቀራረባሉ የሚባሉ እስረኞች ላይ ይበረታል። በፍተሻ ወቅት እራሳቸው ሳንሱር አድርገው ያስገቡት መጽሐፍ ሳይቀር ይወሰድብናል። መጽሐፍት ሳንሱር ሰበብ እንዳይገቡ/እንዲመለሱ ይደረጋል። ከሚገቡልን መጽሐፍት የሚመለሱት ይበልጡ ነበር። ሌሎች እስረኞችን በማይመለከት “ሕግ” በመተዳደራችን የተነሳም፤ በእስረኞችም ሆነ በፓሊሶች ዘንድ እንደ ልዩ ፍጡር ነው የምንታየው።

ቤተሰቦቻችንም ሊጠይቁን ሲመጡ የሚደርስባቸው እንግልት ከሁሉ የከፋ ነው። እኛ እስረኞች በመሆናችን የመጠየቂያ ሰዓታችን መቼም ሆነ መቼ ለውጥ የለውም። ጠያቂዎቻችን ግን ከ6ሰዓት በፊት ግቢ ውስጥ መድረስ አለባቸው። አንድ ደቂቃ እንኳን አሳልፈው በር ላይ ቢደርሱ የሚሰማቸው የለም። በዚህ ምክንያት ቤተሰቦቻችን በር ደርሰው ሳያዩን የሚመለሱባቸው ቀናት ጥቂት አይደሉም። በ6ሰዓት ተጠያቂዎች እና ጠያቂዎች ላይ የሚደርሰው በደል ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለም።

በሕገ መንግሥታችን አንቀፅ 21 ላይ በጥበቃ ስር እና ተፈርዶባቸው በእስር ስላሉ ሰዎች መብት ሲያስቀምጥ ምንም አይነት ልዩነት አላስቀመጠም። ወንዶች ጋር ከታዋቂ ጋዜጠኞች፣ የፓርቲ አመራራት እና የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች በስተቀር የስድስት ሰዓት ተጠያቂ የሚባል ነገር የለም። ከተመሳሳይ ወንጀል ከተከሰሱ/ከተፈረደባቸው ወንዶች ጋር እንኳን በእኩል አይደለም እንታይ የነበረው። በዚህም በሕገመንግስቱ አንቀፅ 35 የተደነገገውን የሴቶች ከወንዶች ዕኩል የመታየት መብት የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር መጣሱን ማየት ይቻላል። እነዚህ በሕገ መንግሥት የተደነገጉ መብቶች፤ በማረሚያ ቤቱ አስተዳደር እየተጣሰ እንዳለ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ብናሰማም ተገቢውን ምላሽ አናገኝም። ወይ በማረሚያ ቤት አስተዳደር ጉዳይ አያገባኝም ይላሉ፣ ወይም የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር ምላሽ እንዲሰጥበት ያዛሉ። የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር ኃላፊዎች በአካልም ተገኝተውም፤ በጽሑፍም የስድስት ሰዓት ተጠያቂ የሚባል ነገር እንደሌለ እና ከሌሎች እስረኞች በተለየ አናያቸውም ብለው ዓይን ያወጣ ውሸት ይዋሻሉ። እነዚሁ ኃላፊዎች ወደ ግቢ ሲመለሱ የስድስት ሰዓት ተጠያቂዎች ብለው በማስታወቂያ አስጠርተው ይሰበስቡንና ፍርድ ቤት መናገራችን ለውጥ እንደማያመጣ ይነግሩናል።

ታዲያ እራሱ መንግሥት ለሴቶች አስከበርኩ ያለውን መብት እራሱ እየጣሰ፤ ግን ደግሞ በየዓመቱ የሴቶች ቀን እያለ ስለ ሴቶች መብት መደስኮር በፍፁም የማይጣጣም እና የኢሕአዴግን መንግሥት ግብዝነት የሚያሳይ ነው።

በቃሊቲ የስድስት ሰዓት ተጠያቂ የነበሩ እንዲሁም አሁንም እዛው ያሉ ሴት እስረኞች* ዝርዝር የሚከተሉት ናቸው።

  1. እማዋይሽ ዓለሙ– በ2001 ሚያዚያ ወር ጀምሮ በእስር ትገኛለች። መፈንቅለ መንግሥት ለማድረግ ተንቀሳቅሳችኋል በመባል በእነ ብርጋዴል ጀኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ ከተከሰሱት ውስጥ አንዷ ስትሆን የዕድሜ ልክ ፍርድ ተፈርዶባት በቃሊቲ የምትገኝ ነች።
  2. ሒሩት ክፍሌ -ከ2003 ሰኔ ወር ጀምሮ በእስር ትገኛለች። በነኤልያስ ክፍሌ መዝገብ ከተከሰሱት 5 ሰዎች አንዷ ናት። የሽብር ክስ ተመስርቶባት 14 ዓመት ተፈርዶአባት በቃሊቲ የምትገኝ ነች።
  3. ጫልቱ ታከለ – ትውልዷእና ዕድገቷ ምስራቅ ወለጋ ነው። ከኦነግ ጋር ግንኙነት አላችሁ ተብለው በ2000 ከታሰሩ በርካታ ኦሮሞዎች መሃከል አንዷ ናት። የተፈረደባት 12 ዓመት ሲሆን፤ ከ7ዓመት በላይ በእስር አሳልፋለች። አሁን በቃሊቲ ትገኛለች።
  4. ባጩ መርጋ -የ18 ዓመት ፍርድ ተፈርዶባት በቃሊቲ የምትገኝ።
  5. ቢፍቱ -የ18ዓመት ፍርድ ተፈርዶባት በቃሊቲ የምትገኝ።
  6. ድርቤ (ቦንቱ) ኢታና -በ2002 በራሷ ሥም በተከፈተው መዝገብ (እነ ድርቤ ኢታና) ከተከሰሱት 7 ሰዎች አንዷ ስትሆን የሞት ፍርድ ተወስኖባት በቃሊቲ የምትገኝ።
  7. ኡርጌ አበበ -በ2002 እነ ድርቤ ኢታና መዝገብ ከተከሰሱት 7 ሰዎች አንዷ ስትሆን የሞት ፍርድ ተወስኖባት በቃሊቲ የምትገኝ።
  8. ሃዋ ዋቆ – የቦረና ልጅ ናት። በ2003 በነበቀለ ገርባ መዝገብ ከተከሰሱት 9 ሰዎች አንዷ ናት። በሽብር ተከሳ 5 ዓመት ተፈርዶባት የነበረ እና በ2007 ግንቦት ወር አካባቢ ፍርዷን ጨርሳ የወጣች።
  9. ሂንዲያ ኢብራሂም – የሶማሌተወላጅ ስትሆን በሽብር ወንጀል ተከሳ 6 ዓመት ተፈርዶባት የነበረ። ባለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር አካባቢ ፍርዷን ጨርሳ የወጣች።
  10. ኡሜማ አሕመድ -የሶማሌ ተወላጅ ስትሆን በሽብር ወንጀል ተከሳ 6 ዓመት ተፈርዶባት የነበረ። ባለፈው ዓመት ሚያዚያ ወር አካባቢ ፍርዷን ጨርሳ የወጣች።
  11. አበራሽ ኢቲቻ -በ2000 ላይ ለኦነግ የገንዘብ ዕርዳታ በማድረግ እና የኦነግ አባል ናችሁ ተብለው በነኢንጂነር መስፍን አበበ መዝገብ ከተከሰሱት 16 ሰዎች ውስጥ አንዷ ናት። አስር ዓመት ተፈርዶባት በ2007 ሰኔ ወር ላይ ፍርዷን ጨርሳ ከእስር ተለቃለች።
  12. ህደያ ከድር -በ2006 ነሐሴ ወር በረመዳን ፆም ወቅት ተቃውሞ በነበረባቸው ጁምአ ቀናት በአንዱ ቀን ከመንገድ ላይ ተይዛ ከእህቷ ራቢያ ከድር ጋር የታሰረች። 5ወር ተፈርዶባት የነበረ ሲሆን ፍርዷን ጨርሳ የወጣች።
  13. ራቢያ ከድር -በ2006 ነሐሴ ወር የረመዳን ፆም ወቅት ተቃውሞ በነበረባቸው ጁምአ ቀናት በአንዱ ቀን ከመንገድ ላይ ተይዛ ከእህቷ ህደያ ከድር ጋር የታሰረች። 5ወር ተፈርዶባት የነበረ ሲሆን ፍርዷን ጨርሳ የወጣች።
  14. ሃያት አሕመድ – ከሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ጋር በተያያዘ ከአዳማ ከተማ ከተያዙ ሙስሊሞች አንዷ ናት (በእነ አብዱላዚዝ መዝገብ)። በ2005 የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስዳ ውጤቷን በመጠባበቅ ላይ እያለች ነው የድንገቴ እስር የገጠማት። በእስር ሆና ክሷን ለዓመት ከስምንት ወር ስትከታተል ቆይታ በነፃ ተለቃለች። (ማእከላዊ 4 ወር ቆይታለች)
  15. ፈቲያ መሐመድ – ከሙስሊምመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጋር በተያያዘ ከአዲስ አበባ እና ከሌሎች ዩንቨርስቲ እና ኮሌጅ ተይዘው ከታሰሩት ውስጥ ናት። ለዓመት ከስድስት ወር ያክል ክሷን በእስር ሆና ስትከታተል ቆይታ 6 ወር የተፈረደባት ሲሆን ከተፈረደባት የፍርድ ልክ በላይ በእስር በመቆየቷ በጥቅምት ወር 2007 ከእስር ወጥታለች። (ማእከላዊ 4 ወር ቆይታለች)
  16. መርየም ሐያቱ -ከሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጋር በተያያዘ ከአዲስ አበባ እና ከወልቂጤ ኮሚቴውን ለመተካት ሲንቀሳቀሱ ነበር ተብለው ከተያዙት (እነ ኤልያስ ከድር) ውስጥ አንዷ ናት። መርየም በ2005 መጨረሻ አካባቢ ከወልቂጤ ነው የተያዘችው። ከሁለት ዓመት አራት ወር የፍርድ ቤት መንከራተት በኋላ በታኅሳስ ወር 2008፣ 7ዓመት ተፈርዶባት ቃሊቲ የምትገኝ። (ማእከላዊ 4ት ወር ቆይታለች)
  17. ሃያተልኩብራ ነስረዲን – ከ5ት ወር የማዕከላዊ ቆይታ በኋላ ‹የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ› የተባለ ‹የሽብርተኛ ድርጅት› ጋር ግንኙነት በማድረግ በሚል ሐምሌ ወር 2007 ላይ ክስ ከተመሰረተባቸው 20 ሰዎች ውስጥ አንዷ ሆና ቃሊቲ እስር ቤት ገባች። ከወራት በፊት ችሎት እንዲቀየርላቸው ያመለከቱ ሲሆን፤ እስካሁን አቤቱታቸው ባለመመለሱ የዐቃቢ ሕግ ምስክሮችን መሰማት አልተጀመረም።
  18. 18. ኤዶምካሳዬ(ጋዜጠኛ) – በሚያዚያ 17/2006 ተይዛ ማዕከላዊ ለሦስት ወራት ከቆየች በኋላ ክስ ተመስርቶባት ቃሊቲ እስር ቤት ገባች። የኅብረተሰቡን ደኅንነት አደጋ ላይ ለመጣል አሲራችኋል፣ አቅዳችኋል ተብለው በነሶሊያና ሽመልስ መዝገብ ከተከሰሱት 3 ጋዜጠኞች አንዷ ስትሆን ለዓመት ከሦስት ወር በእስር ሆና ክሷን ከተከታተለች በኋላ ክሱ ተቋርጦላት በነፃ ወጥታለች።
  19. ማሕሌት ፋንታሁን -በሚያዚያ 17/2006 ተይዛ ማዕከላዊ ለሦስት ወራት ከቆየች በኋላ ክስ ተመስርቶባት ቃሊቲ እስር ቤት ገባች። የኅብረተሰቡን ደኅንነት አደጋ ላይ ለመጣል አሲራችኋል፣ አቅዳችኋል ተብለው በነሶሊያና ሽመልስ መዝገብ ከተከሰሱት 6 ጦማሪ አክቲቪስቶች አንዷ ስትሆን ለዓመት ከሦስት ወር በእስር ሆና ክሷን ከተከታተለች በኋላ ክሱ ተቋርጦላት በነፃ ወጥታለች።
  20. ርዕዮት ዓለሙ (ጋዜጠኛ እና መምህርት) – በ2003 ሰኔ ወር ላይ ተይዛ ማዕከላዊ ገባች። በነኤልያስ ክፍሌ መዝገብ በሽብር ወንጀል ከተከሰሱት አምስት ሰዎች አንዷ ናት። ከፍተኛ ፍቤት የ14ዓመት ፍርድ ከበየነባት በኋላ ይግባኝ ብላ ክሶች ተሰርዘውላት ቅጣቱ ወደ 5ዓመት ዝቅ አለላት። በደንቡ መሠረት በአመክሮ ጥቅምት ወር 2007 ላይ መለቀቅ ሲገባት፤ በጥፋቷ መፀፀቷን አምና ካልፈረመች አመክሮ አይሰጥሽም ተባለች። የማላምንበት ነገር ላይ አልፈርምም በማለትም ያለአመክሮ ፍርዷን ለመጨረስ ወሰነች። ባልተጠበቀ እና ባልታሰበ ወቅት ከአራት ዓመት እስር በኋላ ሐምሌ 1፣ 2007 ከእስር ተለቀቀች። የመጨረሻዎቹን ሁለት የእስር ዓመታት አምስት የእሷን ሁኔታ የሚከታተሉ እስረኞች ያሉበት ብቻ በቅጣት ቤት ውስጥ ነበር ያሳለፈችው፤ ከእናት እና አባቷ ውጪም በማንም እንዳትጎበኝ ተከልክላ ነበር። በእስር ሆና ‹የኢሕአዴግ ቀይ እሰክብሪቶ› የሚል የቀድሞ ጽሑፎቿ ስብስብ ታትሞላታል፡፡
  21. ረዳት ኢንስፔክተር አዜብ ተክላይ -ለኤርትራ የስለላ ቡድን የሃገሪቱን ደኅንነት አደጋ ላይ የሚጥል መረጃ አቀብለሻል ተብላ የዛሬ ሁለት ዓመት አካባቢ ማዕከላዊ ገባች። ከአራት ወር በላይ እዛ ከቆየች በኋላ ምንም ማስረጃ ሳይገኝባት በስለላ ወንጀል ክስ ተመሥርቶባት ቃሊቲ እስር ቤት ገባች። ክሷን በእስር ሆና ስትከታተል ቆይታ በዚህ ዓመት መጀመሪያ አካባቢ ጥፋተኛ ተብላ የ7ት ዓመት ፍርድ ተበይኖባታል። ጥፋተኛ መባል አይገባኝም ስትል ጠቅላይ ፍቤት ይግባኟን አቅርባ ተከራክራለች። ለመጋቢት 16/2008 ለብይን ተቀጥራለች።
  22. አበበች ጣሙ –የጎንደር ተወላጅ ናት። በጥር ወር 2006 ላይ ተይዛ ማዕከላዊ ገባች። በእነአበበ ካሴ መዝገብ ከተከሰሱት ውስጥ ስትሆን መሳሪያ ደብቀሻል የሚል ክስ ነው የተመሰረተባት። 1 ዓመት ከአምስት ወር በእስር ቆይታ በ2007 ሰኔ ወር ላይ በዋስ ወጥታ ክሷን ስትከታተል ከቆየች በኋላ ጥር ወር 2008 ላይ በነፃ የተሰናበተች።
  23. እየሩሳሌም ተስፋው -የሰማያዊ ፓርቲ አባል የነበረች። በየካቲት ወር 2007 በሰላማዊ ትግል ተስፋ ቆርጣ ሰማያዊ ፓርቲን በመልቀቅ በኤርትራ በኩል ግንቦት 7 ልትቀላቀል ስትል ማይ ካድራ የተባለ ቦታ ላይ ተይዛ ወደ ማዕከላዊ የገባች። ከዛም የሽብርተኛ ድርጅት አባል መሆን የሚል ክስ ተመስርቶባት በቃሊቲ የምትገኝ። እሷ ያለችበት መዝገብ (እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ) መከላከያ ምስክሮችን ለማሰማት ለመጋቢት 22/2008 ተቀጥረዋል።
  24. እየሩስ አያሌው– የ2007ን ሃገራዊ ምርጫ ተከትሎ “ትግሬ አይገዛንም” ብለሻል የሚል ክስ ተመስርቶባት ዓመት ከአራት ወር ተፈርዶባት ግንቦት ወር 2007 ላይ ቃሊቲ ገባች። ከፍተኛ የአይምሮ ጭንቀት ሕመም የነበረባት ሲሆን ምግብም አትበላም ነበር። በየካቲት ወር መጀመሪያ 2008 ላይ በእስር ላይ እያለች እራሷን አጥፍታ ሕይወቷ ያለፈ።
  25. ቀለብ ስዩም -ከአራት ወር በላይ ይሆናታል ከታሰረች። ከጎንደር ነው የመጣችው። በሽብር ወንጀል ተከሳ ጉዳይዋን በቃሊቲ እስር ቤት ሆና እየተከታተለች የምትገኝ።

26 ሃዊ ጎንፋ -በሽብር ወንጀል ተከሳ ሦስት ያልተገቡ ዓመታትን በእስር አሳልፋለች። ለሦስት ዓመታት ክሷን በእስር ሆና ስትከታተል ከቆየች በኋላ በነፃ ተሰናብታለች። በማዕከላዊ እና ቃሊቲ የታዘበችውን የሚተርክ RIRRIITTAA የተሰኘ መጽሐፍ እና ሌሎች ሁለት ተጨማሪ መጽሐፍቶችን (HIREE GALGALAA እናCANCALA QABSOO) አበርክታለች።

  1. አየለች አበበ -ካጋሞ ጎፋ ዞን ተይዘው አራት ወር ማዕከላዊ ከቆዩ በኋላ የሽብርተኛ ቡድን አባል ናችሁ በመባል በሚያዚያ 27 ቀን 2008 ክስ ከተመሠረተባቸው የሰማያዊ ፓርቲ አባላት (እነ ሉሉ መሰለ) ውስጥ ናት።

የISIS ቡድን በሊቢያ ኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን ግድያ በመቃወም በሚያዝያ ወር 2006 በተጠራው ሰልፍ ጋር በተያያዘ “ስብሰባ በማወክ”፣ “ሁከት በመፍጠር”፣ እና በመሳሰሉ ክሶች የተመሠረተባቸው በርካቶች ናቸው፡፡ ከነዚህ ውስጥ ጭራሽ ሰልፉ ላይ ያልነበሩ (እቤታቸው ወይም ሥራ ገበታቸው ላይ የነበሩ) ይገኙበታል፡፡ በነጻ የተሰናበቱት እንዲሁም ስምንት ወር ፍርድ ተወስኖባቸው የነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ቅጣታቸውን ጨርሰው ከእስር ወጥተዋል፡፡ ቃሊቲ ገብተው የነበሩት የሚከተሉት ናቸው፡፡

  1. ብሌን መስፍን – (የሰማያዊ ፓርቲ አባል)
  2. ቤተልሔም አካለወልድ
  3. ወይንሸት ሞላ (የሰማያዊ ፓርቲ አባል)
  4. ዝናሽ አንከላ
  5. ዝናሽ ምትኩ
  6. ማሕሌት ኤርሳዶ
  7. እኑኪ ኃይሉ
  8. ቤዛዊት ግርማ (ጋዜጠኛ)
  9. ራሕሙ ጀማል
  10. ፍቅር
  11. መስከረም ወንድማገኝ (አርቲስት)
  12. ዮዲት ኃይለማርያም
  13. ሔለን ነዋይ
  14. ሜሮን አስማማው
  15. ንግሥት ወንዲፍራው (የሰማያዊ ፓርቲ አባል)

—-

*በመረጃ እጦት የተገደፉ ጥቃቅን ስህተቶች እና ያላካተትኳቸው እስረኞች ሊኖሩ ይችላሉ።

 

Source: Zone9blog

በኦሮሚያ ዘገባ ለማቅረብ የተንቀሳቀሱ ጋዜጠኞች በቁጥጥር ስር ውለው ተለቀቁ – VOA

$
0
0

በኢትዮጵያ ሁለት ዓለምአቀፍ ጋዜጠኞችና አስተርጓሚያቸው በኦሮሚያ የተከሰተው ድርቅና የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ዘገባ ለማቅረብ ሲንቀሳቀሱ ለ24 ሰዓታት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታወቁ።

የብሉምበርግ የዜና ምንጭ ዘጋቢ ዊሊያም ዴቪድሰን፣ ለተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን የምትዘግበው ጄሲ ፎርትንና አስተርጓሚያቸው በኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች ያለምንም ማብራሪያ ከአዋሽ ከተማ ወደ አዲስ አበባ በፌዴራል ፖሊስ ታጅበው እንዲመለሱ ከተደረገ በኋላ አዳር ታስረው መለቀቃቸውን አቅታውቀዋል።

ጋዜጠኞቹ ወደ ኦሮሚያ ክልል ያመሩት ባለፈው ሮብለት ሲሆን፤ ቀዳሚው ቆይታቸው በአዳማ ዩኒቨርስቲ ነበር። በዩኒቨርስቲው ተማሪዎችን በተለይ በኦሮሚያ የሚካሄዱ የተቃውሞ ሰልፎችን አስመልክቶ የብሉምበርግ ዘጋቢ ዊሊያም ዴቪድሰንን አነጋግረንው ነበር።

ሐሙስ ጠዋት ተነስተው ወደ ምስራቅ ኢትዮጵያ አመሩ። የጉዟቸው አላማ በምእራብ ሐረርጌ በቅርቡ በአሰቦች ሒርናና ሌሎች ከተሞች የተቀሰቀሱ ሰልፎችን አስምልክቶ ሁኔታውን ለመከታተልና ለመዘገብ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን በመጉዳት ላይ ያለው ድርቅ፤ በምእራብ ሀረርጌ ያስክተለውን ጉዳትም ለመመልከትና ለመመዘን እንደሆነ ዊሊያም ዴቪድሰን ያስረዳል።

በአዋሽ ከተማ ምሳ በልተው ከከተማ ወጣ እንዳሉ፣ “ከምሥራቅ ወደ ደቡብ ምሥራቅ እያመራን ሳለ፤ አንድ የፍተሻ ጣቢያን አለፈን ከዚያ በኋላ የፌደራል ፖሊስ መኪና የኛን መኪና አስቆመንና (የኔ የራሴ መኪና ነበር ይዤ የነበር የምጓዘው) ከሌላ የውጭ ጋዜጠኛ እና ከ አስተርጓሚ ጋር፣ ፌደራል ፖሊሶች ፓስፖርታችንን፣ የመኖርያ ፍቃዳችንና ዜግነታችንን እንድሳይ ጠየቁን ።” ይላይ ዊልያም።

ለተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ዘገባ የምታቀርበው ጄሲ ፎርትን እና ኢትዮጵያዊ አስተርጓሚያቸው ነበሩ በመኪናው ውስጥ። በወቅቱ ከጸጥታ ባለስልጣኖችም ሆነ ከያዟቸው የፌዴራል ፖሊስ ባልደረቦች ለምን እንደተያዙ በህግም ሆነ በአሰራር ተጠቅሶ የተነገራቸው ምንም አይነት ነገር እንደሌለ ዊሊያም ዴቪድሰን ለቪኦኤ አስረድቷል።

የብሉምበርግ የዜና ምንጭ ዘጋቢ ዊሊያም ዴቪድሰንየብሉምበርግ የዜና ምንጭ ዘጋቢ ዊሊያም ዴቪድሰን

በአዋሽ የነበራቸው ቆይታ አጭር ነበር በጥቂት ደቂቃዎች ወስጥ፣ “በፖሊስ ታጅበን ወደ አዲስ አበባ እንድንመለስ ተወሰነ።  ውሳኔው በ10 ደቂቃ ውስጥ ነው የተወሰደው።” በማለት ገልጾልናል ዊልያም።

በተጨማሪም “ምን እንዳጠፋን የሚገልጽ ምልክት አልነበረም። ምን እንዳጠፋንም ግልጽ አልነበረም። በቀጥታ የምናነጋግራቸው የነበርንው ሰዎች ግን ትእዛዝ እንደተሰጣቸው ብቻ ነው የነገሩን።” ብሏል።

 

ጄሲ ፎርትንጄሲ ፎርትን

ከዊሊያም ዴቪድሰን ጋር የታሰረችው ጄሲ ፎርትን በትዊተር ገጿ፤ “በኢትዮጵያ ዘገባ ሳቀርብ አዳሬን ታስሬ ነበር” በማለት የምስራቅ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞች ማህበር ያወጣውን መግለጫ አካታለች።

የምስራቅ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞች ማህበር በኢትዮጵያ በመገናኛ ብዙሃን ነጻነት ዙሪያ የሚታዩ ጥሰቶች ክፉኛ እንዳሳሰቡት አስታውቋል።  በኢትዮጵያ ፈቃድ አውጥተው የሚንቀሳቀሱ የውጭ ሀገር ጋዜጠኞች እንዲሁ በዘፈቀደ ለአጭር ጊዜ በቁጥጥር ስር እየዋሉ፤ ስራቸውን እንዳይሰሩ ሆን ተብሎ ይደረጋል፤ አሰራሩም የመገናኛ ብዙሃን ነጻነትን ይጥሳል ብሏል ማህበሩ። ኢልያ ግሪንደርፍ የድርጅቱ የቦርድ ሃላፊ ናቸው።

“ጋዜጠኞችን ማሰር የሚጠቅማቸው አይደለም። አነጋጋሪና ጥንቃቄ በሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ (ለምሳሌ እንደ ኦሮሚያ ተቃውሞዎች ያሉ) ጋዜጠኞች ዘገባ እንዳያቀርቡ ማስቆም የሚያመጣው ፋይዳ የለም። በጣም የሚያሳስበንና ድምጻችንን እንድናሰማ የሚያስገድደን ሁኔታ አለ። የኢትዮጵያ መንግስት ከለት ወደለት በመገናኛ ብዙሃና ላይ የሚያከናውነውን አፈና እያጠናከረ ሲሄድ ተመልክተናል። በተመሳሳይ ወቅት ኢትዮጵያ ባለሃብቶችን በመሳብ ላይ ትገኛለች። በአፍሪካ ሁለተኛው ትልቅ የህዝብ ብዛት ወዳላት ሀገር  የምጣኔ ሀብቱን እድገት ተከትሎ፤ በስፋት ወደ ኢትዮጵያ ስራ ለመስራት  የንግዱ ማህበረሰብ በመትመም ላይ የገኛል። የሚይድጉ ሀገሮች እንደ ዩናይትድስ ስቴይትስ፣ ብርታንያና አውስትራሊያ የመሳሰሉ አይነት የመብትና የአሰራር ደረጃ መኖር እንዳለበት እናምናለን።” ብለዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት በጉዳዩ ላይ እስካሁን የሰጠው መግለጫ የለም። ከፍተኛ የመንግስቱን ባለስልጣናት ለማግነት ሞክረን አልተሳካልንም።

ሔኖክ ሰማእግዜርና ሳሌም ሰለሞን ጉዳዩን ተከታትለው ያቀረቡትን ዘገባ ለማዳመጥ የድምጽ ፋይሉን ይጫኑ።

 


የጉልበት ሰጪው እጽ ጉዳይ |“በአንድ በመንደር ልጆች የተያዘው ስልጣንን ተገን ያደረገው ባለሙያ አልባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ይፍረስ”| Audio

$
0
0

“…እነ አበበ ቢቂላ ፣ማሞ ወልዴ፣ፋጡማ ሮባ፣ደራርቱ ቱሉ፣ምሩጽ፣የዲባባ ልጆች፣እነ ሀይሌ ፣ቀነኒሳና ሌሎቹም አገራቸውን በክብር እንዳላስጠሩ ዛሬ አበረታች እጽ በመውሰድ ስማቸው የሚጠራ አትሌቶች መኖራቸው ያሳፍራል በአንድ በመንደር ልጆች የተያዘው ስልጣንን ተገን ያደረገው ባለሙያ አልባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ይፍረስ…”

አ/አ ውስጥ በገሃድ ሲሸጥ ከርሞ ለእውቅ እና ለብርቅዩ አትሌቶቻችን እንቅፋት የሆነው በአለም ላይ የታገደው ጉልበት ሰጪ መድሐኒት ያሰከተለው ብሔራዊ እና ዓለማቀፋዊ መዘዝ ሲዳሰስ:: ታምሩ ገዳ አሰናድቶታል ያድመጡት::

doping copy

የአሜሪካ አከራካሪና አስተዛዛቢ አቋም –በአጼ ሀይለስላሴ፣ በደርግና በወያኔ ዘመን |ከኤርትራ መገንጠል በፊትና በኋላ (ልዩ ዘገባ)

$
0
0

የአሜሪካ አከራካሪና አስተዛዛቢ አቋም – በአጼ ሀይለስላሴ፣ በደርግና በወያኔ ዘመን | ከኤርትራ መገንጠል በፊትና በኋላ ዲፕሎማሲዋና ድጋፉዋና ማዘናጊያዋ የቀድሞ ዲፖሎማቶቿ ምስክርነት ሲፈተሽ (ልዩ ዘገባ )
አዘጋጅና አቅራቢው ለሕብር ራድዮ አብይ አፈወርቅ ነው::

mengistu hailemariam

“የማንነት ጥያቄ በሃይል አይገታም”–በሰሜን አሜሪካ ከሚኖሩ የጠለምት ተወላጆች የተሰጠ መግለጫ

$
0
0

 

Telemet
የካቲት 30 ቀን 2008 ዓ/ም ኢትዮጵያን በማፈራረስ፣ ሃብቷን በመዝረፍ፣ ሕዝቧን በማሳደድ፣ በማፈናቀልና በማሰቃየት ለ 25 ዓመታት ያህል በመሳርያ
ሃይል አስገድዶ በመግዛት ላይ ያለው ጠባብ በሄርተኛው ወያኔ፣ በሕዝብና በአገር ላይ እየፈፀመ ያለው ግድያ፣ እስራት፣ እንግለት፣ሰቆቃና ግፍ በቀላል ቋንቋ ለመግለጽ ያዳግታል።
ገና ጫካ እያለ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት ቃለ መሃላ አድርጎ የመጣው ዘረኛው ወያኔ በሕዝብና በሃገር ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት መቆምያ አጥቶ እጅግ አሳሳቢና አደገኛ ደረጃ ላይ ደርሷል።

ታላቋን ትግራይ ለመመሥረት በሚል ፀረ ኢትዮጵያ አቋም የተመረዘው ወያኔ(ህውሃት) በለምነታቸዉ፣ በተፈጥሮ ሃብት ጠቃሚነታቸው ዉብ በሆኑ ወንዞችና ጅረቶች የተከበቡና እስትራቴጅካዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ቦታዎች ለትግራይ ክ/ሃገር አጎራባች ከሆኑት ክፍላተ-ሀገራት ወደ ትግራይ ክልል ማስገባቱን ይታወቃል።

ወያኔ ኢትዮጵያን በጠመንጃ ሃይል ስልጣን ከተቆጣጠረበት ከ1983 ዓ/ም ጀምሮ የታላቋን ትግራይ ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግ ለምና ወሃ-ገብ የሆኑትን የጎንደር ወረዳዎች፣ ወልቃይት፣ ጠገዴንና ጠለምትን ከወሎ ክ/ሃገር ደግሞ ወደ አራት የሚሆኑ ወረዳዎችን በትግራይ ክ/ሃገር ሥር እንዲሆኑ አድርጓል;

ጠለምት፣ በረጅሙ የኢትዮጵያ ታሪክ በጎንደር ክ/ሃገር የሚገኝ አማራ፣ የአማራ ባህልና ወግን የሚከተል ሕዝብ ለመሆኑ ታሪክ ያረጋገጠው ሃቅ ነው። የጠለምትን መልከዓ-ምድር አቀማመጥን ስንመለከት፤ በሰሜን ተከዜ ወንዝን ተከትሎ ትግራይ፤ ክ/ሃገርን በምሥራቅ እንዲሁ ተከዜን ወንዝን ተከትሎ ተንቤን አውራጃ(ትግራይ) እና ዋግ አውራጃ(ወሎን)፤ በምዕራብ ወልቃይትና ጠገዴ፤ በደቡብ በተፈጥሮ ሃብት የበለጸጉ በጎንደር ክፍለ-ሃገር የሚገኙ የሰሜን ተራራዎች ስንሰለት ያዋስናል።

የተለያዩ የውጭ ወራሪ ጠላቶች በተለያዩ ጊዜያት አገራችን ኢትዮጵያ ለመውረር ሲመጡ፤ ጀግናው የጠለምት ሕዝብ የአገሩን ነፃነትና ዳር ድንበር ለማስከበር በተለያዩ የጦር ሜዳዎች በቆራጥነት በመዝመት በኢትዮጵያ ታሪክ ምዕራፍ ውስጥ ታላቅ አንጸባራቂና አኩሪ ታሪክ የሠሩ፤ በ5 ዓመት የጣሊያን ወረራ ጦርነት ወቅት ከፍተኛ ጀብዱ የፈፀሙ እውቅና ስመ ጥር አርበኞችን ያፈራ ሕዝብ ነው።

የጠለምት ሕዝብ ልክ እንደ ወገኖቹ ወልቃይትና ጠገዴ ሕዝብ ከትግራይ ሕዝብ ጋር የሚያዋስነው ተፈጥሮአዊ ድንበር የማይሞተውና የማይዋሸው የተከዜ ወንዝ ሲሆን ረጅሙ ገናናው የኢትዮጵያ ታሪክም የሚመሰክረው ይኸኑን ዕውነታ ነው። ለግንዛቤ ያህል፤ ሩቅ ሳንሄድ፤ በዘመነ መሳፍንት ጊዜ የአማራ ተወላጆች የነበሩ መሪዎች እንደ ራስ ወልደሩፋኤል፣ ልጃቸው ራስ ገብሬ፣ ራሰ ኃይለማርያም እና ደጃዝማች ውቤ ይገዙት የነበረው ግዛት ከባንብሎ (ከጎንደር ከተማ በስተሰሜን በኩል በግምት 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝው ጉርድ መሬት) እስከ ተከዜ ወንዝ ያለውን ሠፊ ግዛት ነበር። ይኸም ሠፊ ግዛት አሁን የምናውቀውን ወገራ አውራጃ (ወገራ፣ ዳባት፣ ጠገዴ፣ ወልቃይትና ሰቲት ወረዳዎች) እና ሰሜን አውራጃ (ደባርቅ፣ ድብባሕር፣ ጠለምት፣ ጃናሞራና በየዳ ወረዳዎች) የሚጠቀልል ነበር። እንድያውም ታላቁ መሪ ደጃዝማች ውቤ ይገዙት የነበረው ግዛት ይህ ብቻ ሳይሆን፤ ትግራይንና ባሕረ-ነጋሽን (ኤርትራን) ጨምሮ ነበር።

ዘመነ መሳፍንት አክትሞ፤ ታላቁና ገናናው የኢትዮጵያ መሪ በአፄ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግሥት፤ እንዲሁም በአፄ ዮሐንስ አራተኛ፤ በአፄ ምንሊክ፣ በአፄ ኃይለሥላሴ እና በኮሎኔል መንግሥቱ ዘመናት የትግራይና የጎንደር አማራ ሕዝብ ተፈጥሯዊ ድንበር ተከዜ ወንዝ እንደሆነ ታሪክ ያረጋገጠው ሃቅ ከመሆኑም ባሻገር የትግራይ ነፃ አውጪ ድርጅት መስራች አባል የነበሩት ዶ/ር አረጋዊ በርሄ፣ ኢንጅነር ግደይ ዘራዓፅዮን፣ አቶ ገብረመድህን አርአያ፣ አቶ አስገደ ገብረስላሴና የትግራይ ጠቅላይ ግዛት አገረ ገጅ የነበሩት የተከበሩ ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም ያረጋገጡት ነው።

TPLF(ወያኔ) የትግራይ አገዛዝ ተከዜን ወንዝ የተሻገረው “ታላቋን ትግራይ” ለመመሥረት ባቀደው እቅድ መሠረት፤ ለምና ወሃ-ገብ የሆኑትን የጎንደር ወረዳዎችን ወልቃይት፣ ጠገዴና ጠለምትን በተቆጣጠሩበት በ17 ዓመት የሽፍትነት ጊዜና ከ25ዓመት በፊት መላ ኢትዮጵያን በሃይል በመዳፉ ሥር ባሰገባበት ወቅት፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ይወያኔ ታጋይዮች የነበሩና ደጋፊዎቻችወን አምጥቶ በወልቃይት፣ በጠገዴና በጠለምት አስፍሮ ለዘመናት በጋራ አብሮ ይኖር የነበረን ሕዝብ እርስ በርሱ እንዲጋጭና እንዲጠላላ አደረገ።ወደ። የትግራይ ነፃ አውጭ ግንባር (ወያኔ) ከላይ የተገለፁትን ወረዳዎች ተቆጣጠሮ ወደ ትግራይ ክልል ካስገባቸው ከጥቂት ወራት በኋላ ወደ 1983 ዓ/ም መጨረሻ አካባቢ፤ አንድ የወያኔ ባለሥልጣን ታማኝ ካድሬውን ወደ አዳርቃይ ከተማ ልኮ ነበር። ካድሬውም በከተማው የሚገኙትን ታላላቅ አዛውንቶች ስብስቦ በማናገር ላይ እያለ “ የትግራይን ድንበር” እስከየት እንደሆነ ታውቃላችሁ ወይ? ብሎ ሲጠይቅ፤ ንግግሩን በጽሞና ይከታተሉ የነበሩት የአገሬው ሰመ ጥሩ አዛውንት “ ልጄ! የትግራይ ድንበር አልፈህ የመጣኸው ተከዜ ወንዝ ነው” ብለው ነበር የመለሱለት።

TPLF(ወያኔ) ካለፉት 25 ዓመታት ጀምሮ፤ የጠለምትን ሕዝብ በመዳፉ ሥር ካስገባ በኋላ፤ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን እንዲሁም የአማራን ሕዝብ ለማጥፋት ባለው እቅድ መሠረት፤ በጠለምት ያሠፈራቸውን ቅጥረኞችን በማስታጠቅ፤ በጠለምት ሕዝብ ላይ ወደር የሌለው ጭፍጨፋ (genocide) እና የዘር ማጥፋት (ethnic cleansing) በማያቋርጥ ሁኔታ አካሂዷል። እያካሄደም ነው። ይኽ ሁሉ ዘግናኝ ግፍ የተካሄደውና በመካሄድ ላይ ያለው ፤ የጠለምት ሕዝብ የማንነት ጥያቄ በማንሳቱና እኛ አማራ፤ ቋንቋችን አማርኛ ነው፤ ክልላችንም ከላይ በታሪክ ተደግፎ እንደተገለፀው ጎንደር ነው ብሎ ስለጠየቀ ነው።

የጠለምት ሕዝብ የደረሰበትንና የሚደርስበትን ጭፍጨፋ እና የዘር ማጥፋት ወንጀል ለኢትዮጵያ ሕዝብ በተቀናጀ መንገድ ለመግለጽና ለማስረዳት፤ በመታገል ላይ ካለው ወገናችን አጋርነታችን ለማሳየትና ብሎም ለነፃነት፣ ለፍትህና ለዴሞክራሲ ከሚታገልው ስፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በመቆም አስከፊዉንና ዘረኛዉን የወያኔ አገዛዝ ለአንዴና ለመጨርሻ አሽቀንጥሮ እንዲጥል ለመቀስቀስ እንዲረዳ በማስብ፤ እኛ በሰሜን አሜሪካ የምንኖር የጠለምት ተወላጆች አስቸኳይ ስብሰባ አድርገን የሚከተለውን የአቋም መግለጫና ሕዝባዊ ጥሪ አቅርበናል።

1. የአማራ ሕዝብ አካልና የጎንደር ክ/ሃገር ክልል የነበሩት ወረዳዎች(ወልቃይት፣ ጠገዴና ጠለምት) እና የወሎ ለም 4ቱ ወረዳዎች ያለሕዝብ ውሳኔና ፈቃድ በወያኔ አስገዳጅነትና ያለ አግባብ ወደ ትግራይ ክልል እንዲጠቃለሉ መደረጉን እናወግዛለን።

2. በፀረ-ኢትዮጵያው የትግራይ ነፃ አውጭ ግንባር (ወያኔ) ከፍተኛ ጭፍጨፋ (genocide) እና የዘር ማጥፋ ( ethnic cleansing) የተካሄደበትና የሚካሄድበት ጀግናው አማራው የወልቃይትና የጠገዴ ሕዝብ ከወያኔ አስከፊና ዘግናኝ አገዛዝ ለመውጣት የሚያካሂደውን ትግልና የአማራ ማንነት መብት ጥያቄ ሙሉ በሙሉ እንደግፋለን፤ እስከ መጨረሻው ድረስ ከጎኑ እንቆማለን።

3. የተቀደሰውና ታሪካዊው ዋልድባ ገዳም በትግራይ ነፃ አውጭ ግንባር (ወያኔ) መደፈር፣ መዘረፍ፣ምፍረስ፣ የአረጋዊ አባቶች መንገላታት፣ መሰደድና መገደል በጥብቅ እናወግዛለን። የወያኔ ጣልቃ ገብነትን እያወገዝን በቅዱስ ገዳምት ያሰፈረዉን ወታደራዊ ሃይል እንዲያነሳና እኩይ ተግባሩን እንዲያቆም እናሳስባለን።

4. እርዝመቱ 1600 ኪ/ሜትር የጎን ስፋቱ ከ20 እስከ 60 ኪ/ሜትር የሆነውን ለም ወሃ-ገብ የአገራችን ዳር-ድንበር መሬት የትግራይ ነፃ አውጭ ግንባር (ወያኔ) በገጸ-በረከት መልክ ለሱዳን መስጠቱ አጥብቀን እናወግዛለን።

5. በኦሮምያ ክልል በኦሮሞ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ላይ እየተፈፀመ ያለዉን ግድያ፣ ጭፍጨፋ፣ እስራትና እንግልት በጥብቅ እያወገዝን ገዳዮቹን ለፍርድ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን።

6. የጠለምት ሕዝብ ሆይ! የትግራይ ነፃ አውጭ ግንባር (ወያኔ) አገዛዝን አሽቀንጥረህ በማጣል የአማራ ማንነትህንና የመሬት ባለቤትነትህን ለማስመለስ የጀምርከውን ትግል አጠናክረህ ቀጥል፤ እኛም ልጆችህ እስከመጨረሻው ድረስ ከጎንህ መሆናችን እናረጋግጣለን።

7. በአገር ውስጥና በውጭ የምትኖሩ የጠለምት ተወላጆች በሙሉ በያላችሁበት በመሰባሰብና በመደራጀት፤ የትግራይ ነፃ አውጭ ግንባር (ወያኔ) በወገናችን የጠለምት ሕዝብ ላይ የሚያካሂደውን ጭፍጨፋ (genocide) እና የዘር ማጥፋት (ethnic cleansing) በማጋለጥና፤ ከወያኔ ጨቋኝ አገዛዝ ቀንበር ነፃ ለመውጣት የሚያደርገውን ትግል በማንኛው መልክ እንድትድግፉ፤ ጥሪ እናቀርባለን።

8. የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ቅጥረኛ የሆነውን ፀረ-ኢትዮጵያው የትግራይ ነፃ አውጭ ግንባር (ወያኔ) እና ተላላኪዎቹን በመራራ ትግላችን አስወግደን፤ እኩልነት፣ ፍትህና የሕግ የበላይነት የሰፈነበት ስርዓት ለመመሥረት እንደ ሰደድ እሳት በመቀጣጠል ላይ ያለውን ሕዝባዊ አመጽና ትግል በማጠናከር በጋራ እንድትታገል አገራዊ ጥሪ እናቀርባለን።

ያለ አግባብ ከጎንደር የተወሰደው መሬት በመራራው ትግላችን ይመለሳል!
የወልቃይት፤ የጠገዴና የጠለምት ሕዝብ የአማራ ማንነት መብት ጥያቄ በቆራጥ ትግላችን እውን ይሆናል! ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
E-mail: telemtgondar@gmail.com

በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢዋ ለምትገኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ጥሪ |የዶ/ር ማይገነት ሽፈራው የክብር ፕሮግራም ላይ ተገኙልን

$
0
0

Dr. Maigenet English and Amharic (1)
በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢዋ ለምትገኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ጥሪ | የዶ/ር ማይገነት ሽፈራው የክብር ፕሮግራም ላይ ተገኙልን

ከጠመንጃ ‘ነፃነት’ ወደ ስኳር ባርነት! |ታሪኩ አባዳማ

$
0
0

ታሪኩ አባዳማ – የካቲት 2008

ለስኳር ማምረቻ ፋብሪካዎች ማስፋፊያ በሚል ሰበብ መጠነ ሰፊ መሬት ከዜጎች እየተዘረፈ መሆኑን ስንሰማ ቆይተናል። የታሪክ እና እምነት መናኸሪያ ዋልድባ ገዳም በይዞታው ስር የሚገኘውን ርስት በዚህ ምክንያት መቀማቱንም እንደ ዋዛ ሰምተን ነበር። ሰሞኑን በምናገኘው ወሬ ደግሞ የኦሞ ሸለቆ ልዩ ልዩ ብሔረሰብ ኢትዮጵያውያን ከክልላቸው ጭካኔ በተመላበት የወያኔ አስገድዶ ማፈናቀል ዘመቻ ከቄያቸው ሲጋዙ መክረማቸውን ተረድተናል። መሬታቸው ለሸንኮራ እርሻ ማምረቻ እና ስኳር ፋብሪካ ስለተመረጠ እነሱ ወዳልመረጡት አካባቢ በጠመንጃ አፈሙዝ ተገደው ተወስደዋል።

12801147_966036103443554_4958790932868175941_n

እንደ እንሰሳ በገመድ ተጠፍሮ ካሚዮን ላይ የተጫነውን ወገናችንን አተኩራችሁ ካስተዋላችሁ በስኳር ገበያ የጎመዘዘው የኦሞ ሸለቆ ክልል ህዝቦች ህይወት ስዕል ቁልጭ ብሎ ይታያችሁዋል። ስኳር የሚልሱ ጉልበተኛ ገዢዎች በዜጎች ጉሮሮ እንቆቆ እያንቆረቆሩ ስለመሆኑ በማያሻማ ሁኔታ ትገነዘበላችሁ። ለም የተባለ ያገሪቱ ምድር እንደ ጠላት ወረዳ ወረራ እየተፈፀመበት የይዞታው ባለቤት የሆኑ ነዋሪዎቹ ወደ ዘቀጠ ኑሮ እየተወረወሩ ይገኛሉ። በዚህም የወያኔ እውነተኛ ተፈጥሮ ይበልጥ ግጥጥ ብሎ ወጥቷል።

በመሰረቱ የዚህ አይነቱ ጭካኔ በወያኔ ወህኒዎች በታገቱ ንፁሀን ዜጎች ላይ ሲፈፀም የቆየ በመሆኑ ለብዙዎቻችን እንግዳ ነገር አይደለም። ምናልባት ይህን የተለየ የሚያደርገው በጠመንጃ አፈሙዝ ብሔረሰባዊ ነፃነታችሁ ተረጋግጧል የተባሉት ኢትዮጵያውያን በስኳር ኢንቨስተሮች ጡንቻ እውነተኛ ባርነት ተጭኖባቸው ማየታችን ሊሆን ይችላል –

ወያኔ በስኳር ገበያ ሊከብር ፣ ሊናጥጥ ፤ የወያኔ ጀሌ በስኳር ህይወቱን ሊያጣፍጥ ሌላው ዜጋ አያት ቅድም አያቱ ከተከሉት ከገዛ መሬቱ ላይ በወታደር ተገዶ ይጋዛል – እንደ ከብትም ታስሮ ፣ ተወግሮ እና ተዋክቦ ፤ ስብእናው ተክዶ እና ተዋርዶ የህይወት ተስፋው ጨልሞ ደብዛው እንዲጠፋ ሲደረግ ቆይቷል።

ስኳር መራራ የሆነበት ዜጋ ሆነን የመገኘታችን ምስጢር መፍትሔ ያሻዋል።

የኦሞ ሸለቆ ሰላማዊ ዜጎች ለም መሬታቸውን መቀማታቸው አልበቃ ብሎ በቁማቸው አሳር እንዲቀበሉ በመደረግ ላይ ነው። ወልቃይት ላይ የተፈፀመውን አይን ያወጣ ወረራ ስናስብ ፣ በኦሮሞ ክልል የተፈፀመው የመሬት ዘረፋ እና ማፈናቀል ፣ ጋምቤላ አፅመ ርስቱን የተቀማው ህዝብ – ይህ ሁሉ ድርጊት አፈፃፀሙ ወጥነትና እና ተመሳሳይነት እንዳለው መገንዘብ አያዳግትም። የዚህ እርምጃ ግብ አንድ ጠገብኩ የማይል ስግብግብ ጎጠኛ ሀይል መጠነ ሰፊ ሀብት አግበስብሶ አገዛዙን አለገደብ ማራዘም እንዲበቃ ማስቻል ነው።

ወያኔ የስልጣንና ሀብት ጥሙን ለማርካት ሲል ይሉኝታ የማያውቅ ፣ ስለ ዜጎች ደህንነት ቅንጣት ሀላፊነት የማይሰማው ፣  የሚሊዮኖች ህይወት ቢናጋ ፣ ሰብአዊ ክብራቸው ቢዋረድ… ብሎም ኢትዮጵያ ራሷ ከገፀ ምድር ብትጠፋ ቅም የማይለው መሆኑን በወሬ ሳይሆን በተግባር ሲያሳየን ቆይቷል። ይኼ ዛሬ ያየነው  ድርጊት ሌላ ተጨማሪ ኤግዚቢት ነው። የብሄረሰቦችን እኩልነት አውጃለሁ ብሎ ዘገር የነቀነቀው ባለ ቁምጣ የብሄረሰቦችን ለም መሬት በዘገር እየቀማ ለባርነት እየዳረጋቸው ነው።

የኦሞ ሸለቆ በሞላሰስ አተላ ሲበከል አናይም ያሉ ዜጎች ደማቸው እንደ ጅረት እየፈሰሰ ነው። በወያኔ ወታደር ተገደው ካሚዮን ላይ የተጫኑትን ወገኖቻችንን አካል አስተውሉት ፣ እርቃን ገላቸውን በህሊናችሁ ዳሱት ፣ የፊታቸውን ገፅ አንብቡት ፣ አይናቸውን እዩት – ከግንባራቸው የሚፈሰውን ላብና ደም አስተውሉት… – አንገታቸው ላይ የተሸመቀቀውን ገመድ ፣ ክንዳቸው የፊጥኝ ተሰትሮ መተንፈሻ እንኳ ተነፍገው በጨካኝ ወታደር እርግጫ የሚደርስባቸውን ሰቆቃ አሰላስሉት… እዚህ ፎቶ ላይ ያየናቸው ዜጎች በጥይት ተገድለው በየስርቻው ከተጣሉት የተረፉት መሆናቸውንም አስቡት… ።

አንድ ህዝብ በገዛ አገሩ ይህ ሁሉ ሰቆቃ በቁሙ የሚፈፀምበት ለስንት ስኳር ላሾች ምቾት ሲባል ይሆን?

በማህበራዊ መገናኛ አውታሮች የተለቀቁትን ምስሎች ሳስተውል እስከ አጥንቴ ዘልቆ የሚወጋ ህመም ተሰምቶኛል። ወያኔ ወደ አስራስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የመሳፍንት ዘመን ይዞን የሄደው በፖለቲካ ብቻ ሳይሆን በዚያው በጥንታዊው ዘግናኝ የባሪያ ንግድ ዘዴ አፍሪካውያን የደረሳባቸውን ሰቆቃ በመድገም ጭምር መሆኑን ተገነዘብኩ። ይሄ ነጮቹ barbaric (አረመኔ) የሚሉት ባህርይ ነው። በኔ እምነት ወያኔ በተፈጥሮው barbaric ብቻ ሳይሆን beast (አውሬ) መሆኑን ተገንዝቤያለሁ።

አንድ ኢትዮጵያዊ በገዛ ቄየው እንዲህ እርቃኑን እንደ ከብት ተጠፍሮ ሲንገላታ በአይንህ ብሌን ከመመስከር በላይ ወያኔን የሚገልፅ ምን ትጠብቃለህ። ወደድንም ጠላንም የሚካሄደው ትግል ይህን የባርነት ቀንበር ለመስበር የሚደረግ ተጋድሎ ነው። ይህን ለአፍታ የሚጠራጠር ካለ ሌላ ከዚህ የባሰ ተጨማሪ የዜጎች ውርደት እስኪመጣ ለመጠበቅ የመረጠ ብቻ ነው። ይህም ባርነትን ወዶ እንደ መቀበል ይቆጠራል።

አውሬ ህሊና የለውም – ወያኔ ህሊና የለውም!

ኦሮሞ መሬት ላይ ህፃን ከአዛውንት ፣ ነብሰጡር እናቶች ፣ ለጋ ወጣት ተማሪዎች እና አርሶ አደሮች… ማንም አልቀረውም – ሁሉንም በአውሬ ተፍጥሮው ፣ በመርዛም ጥርሱ ነክሷል… እየነከሰ ነው። ያየናቸው ምስሎች ሀፍረታቸው እንኳ በወጉ ሳይሸፈን በገመድ የፊጥኝ ታስረው በካሚዎን ላይ የታጨቁ ምሬት የተላበሱ ኢትዮጵያውያን በወታደር ሀይል እየተዋከቡ ወደማይውቁበት ስፍራ እየተጋዙ መሆኑን ነው። እነኝህ ዜጎች ምናልባትም በታሪካቸው ከዚህ ቀደም ደርሶ የማያውቅ ጭካኔ እየተፈፀመባቸው ነው። መላ የሰው ዘር ባርነትን በተጠየፈበት በሀያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ነፃነቱን ለምዕተ ዓመታት አስከብሮ የኖረ ህዝብ መልሶ ወደ ባርነት ስርአት ሲገባ ከማየት በላይ ህሊናን የሚያቆስል ጉዳይ የለም።

ኢትዮጵያውያን በባርያ ፈንጋይ እጅ ወድቀናል። ትግላችንን የነፃነት ጥያቄ የሚያደርገውም ይኸው ነው።

ወገኖቻችን በባርነት ቀንበር ስር እየማቀቁ ሳሉ አንዳችንም ከባርነት ነፃ ነን ማለት አንችልም። እንዲህ  አይነቱን አሳፋሪ እና ፀያፍ አውሬአዊ ድርጊት ከምድራችን ለመፋቅ ባለን አቅም እና መንገድ ሁሉ መታገል አማራጭ የለውም።

ተንበርክኮ መኖር ያሳፍራል። የዜጎች ክብር የተዋረደባት ፣ አሳፋሪ አገር ለዛሬውም ሆነ ለነገው ትውልድ አያሻንም። በኢትዮጵያዊነቴ እኮራለሁ እያልን ዜጎቿ ከተራ ሰብአዊ ፍጡር በታች ተዋርደው መሳለቂያ ሲሆኑ ማየት ትልቅ የህሊና ቁስል ነው። ምኑ ነው የሚያኮራን ፣ የኩራታችን ምንጭ የዜጎቻችን ክብር ካልሆነ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live