Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የኢቲቪው ጋዜጠኛ ተመስገን በየነ ተደበደበ

$
0
0

በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ዜናዎችንና መንግስታዊ መግለጫዎችን በማንበብ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ተመስገን በየነ መደብደቡን ጓደኛው ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ አረጋገጠ። ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ “ኤዲቶሪያል ፖሊሲና ዜና አንባቢ ለየቅል ናቸው – ጥቂት ስለ ተመስገን በየነ ጉዳይ” በሚል በፌስቡክ ባሰራጨው መግለጫ የጋዜጠኛውን መደብደብ ማረጋገጡን ገልጾ መደብደቡን ግን አውግዟል።

ጽሑፉ ለግንዛቤ እንዲረዳችሁ በሚል ዘ-ሐበሻ እንደወረደ እንዲህ አቅርባዋለች፦

ኤዲቶሪያል ፖሊሲና ዜና አንባቢ ለየቅል ናቸው -
ጥቂት ነገር ስለ ተመስገን በየነ ጉዳይ

(ከደመቀ ከበደ)

temesgen beyeneከትናንት በስቲያ አንድ ወዳጄ ‹‹ተመስገን በየነ ተደበደበ የተባለው እውነት ነወይ›› ሲል ኢንቦክስ አደረገኝ፡፡ ላጣራና እነግርሀለሁ ብዬው ተለያየን፡፡

****** **** ***** *****
ተመስገንን በቅርበት አውቀዋለሁ፡፡ በጣም ሰላምተኛ፣ ትሁትና ስራውን አክባሪ ነው፡፡ ከውድነህ ክፍሌ ጋር በፋና ኤፍ ኤም 98.1 ላይ የአየር ሰአት ወስደው ይሰሩ በነበረበትና እኔም ከመልቀቄ በፊት ወደ ስቱዲዮ በመጣ ቁጥር የበዛ ትህትናውን እየለመድኩት መጣሁ፡፡ ከዚያ በኋላም ሜሮን ጌትነት፣ አንሙት አብርሀም፣ እሱ /ተመስገን/ እና ሌሎች አምባሳደር ለሆኑለት የልመና ማስወገድ ጉዳይ የተቻለውን ሲያደርግ በዘገባ ጉዳይ ብዙ ተረዳድተናል፡፡ በቃ ስራውን ያከብራል፤ የተሰጠውን ተልዕኮ ለመፈፀም ትጉህና አርአያ ነው – አሁንም ከትህትና ጋር፡፡

ሰሞኑን ስለ እሱ የሰማሁትን በሁለት መልኩ ለማጣራት ጣርኩ፡፡ አንደኛው ከእሱ ከራሱ እና ከባለቤቱ /የቀድሞ ባልደረባዬ እምርታ አስፋው / ጋር ደወልኩ፡፡ የሁለቱም ስልኮች ኦፍ ናቸው በተደጋጋሚ ብሞክርም፡፡ / እስካሁን ድረስ/

ሁለተኛው ከቅርብ ወዳጆቼ እውነቱን ለማጣራት ደወልኩ፤ /ከባለቤቱ ወዳጆችና ከ‹‹አምባሳደርነት›› ወዳጆቹ ማለት ነው፡፡ ከላይ የጠቀስኳቸው ናቸው/
‹‹ጉዳት መድረሱንና ህክምና በመከታተል ላይ›› መሆኑን ነገሩኝ፡፡
‹‹ማን እና ለምን›› ለሚለው ግን መልስ አልነበራቸውም፡፡ ሊኖራቸውም አይችልም፡፡

ከተደጋጋሚ ሙከራዬ በኋላ የባለቤቱ /ከደቂቀቃወች በፈት/ እምርታ ስልክ ጠራ – አነሳችው፡፡
‹‹አሁን በመልካም ጤነነት ላይ ይገኛል፡፡ ትንሽ ቆይተህ ደውልለትና ራሱን አናግረው፤ አሁን ደክሞት ሰለተኛ ነው እንጅ እየተሸለው ነው፡፡›› አለችኝ፡፡
‹‹ምክንያቱ ግን ምንድን ነው›› ስል ደገምኩ ጥያቄዬን፡፡
‹‹አላወቅንም፤ ጉዳዩን ፖሊስ ይዞታል፡፡ ከተጣራ በኋላ እንነግርሃለን›› ብላኝ ‹‹እግዜር ይማረው ብዬ›› ተለያየን፡፡

የሆነውን እስኪ ከሰብአዊነት ብቻ እየመዘንን ‹‹እየተወሩ ያሉ›› ምክንያቶችን እንይ፡፡ ሰብአዊነትን ሰው ከመሆን ጋር ብቻ ሚዛናችን ነው!!

‹‹ተመስገን የተደበደበው በኢቴቪ ዜና የተነሳ ነው›› – እንበል፡፡ ‹‹ማን ደበደበው›› የሚለውን ማጣራቱ ለኔ ፅሁፍ ጠቃሚ አይደለምና ብዙ አልዘላብድም፡፡ ግን ‹‹በኢቴቪ ዜና የተቆጡና የተበሳጩ አካላት ወይም ግለሰቦች ነናቸወው ከተባለ ይሀህ መታየት አለበት፡፡

በሚዲያ ህግ አንድ የሚዲያ ተቋም የሚተዳደረው ‹‹በኤዲቶሪያል ፖሊሲው›› ነው፡፡ የሚዲያ ህገ መንግስት ይባላል፡፡ ይህ ‹‹ኤዲቶሪያል›› እንደየ ሚዲያው ፍላጎት፣ እንደየ ሚዲያው ማሰራጫ አገር፣ እንደየሚዲያው ገዥዎች እሳቤና እውቀት የሚወሰን ነው፡፡ እንደኛ አገር ባሉ ታዳጊ አገራት የሚዲያዎች ኤዲቶሪያል ፖሊሲ ከአገሪቱ ህገ – መንግስት ጋር የተቆራኜ ነው፡፡ የመንግስት ጣልቃ ገብነት ይበዛበታል፡፡ ኢቴቪም ከዚህ የወጣ እንዳልሆነ መንገር ለቀባሪ ማርዳት ይሆናል ፡፡

ታዲያ በማንኛውም ሚዲያ ተቀጥሮ የሚሰራ ሁሉ / ይህ የግል ሚዲያዎችንም ይጨምራል/ ኤዲቶሪያሉን አክብረው የመስራት ግዴታ አለባቸው፡፡ በኤዲቶሪያሉ ያልተስማማ መልቀቅ ብቻ ነው ምርጫው፡፡ ጋዜጠኞች የቤቱ ኤዲቶሪያል ፈፃሚ ሲሆኑ አለቆች ደግሞ አስፈፃሚ ናቸው፡፡
ወደ ዜና አንባቢዎች ስንመጣ ደግሞ፤ ዜና አንባቢዎች የተሰፃቻን ዜናች ያላንዳች መነካካት የሚያነቡ ናቸው – ፖስተኛ ማለት ነው ዜና አንባቢነት፡፡ የተሰጠህን መቀበል ብቻ!!

የሙሉ ጊዜ ዜና አንባቢ / የሚዲያው ቋሚ ተቀጣሪ/ እና የፍሪላንስ ዜና አንባቢዎች አሉ፡፡

ተመስገን በየነ የፍሪላንስ ዜና አንባቢ ነው፡፡ የኢቴቪ ጋዜጠኞች የሰሩትን ዘገባ ከማንበብ የዘለለ ምንም ሚና የሌለው፡፡ እንደ ጋዜጠኛ ወጥቶ መረጃ ቃርሞ ወይ ኤዲት አድርጎ የማቅረብ አንዳች ተልዕኮ የለውም፡፡
ይህን ነው ‹‹ለምን›› እንድል ያደረገኝም ፤ ብዬም ወደእናንተ ያስፃፈኝም ‹‹ይኸወ የአንባቢነት እንጅ የመረጃ ቃራሚነት ወይም ሃያሲነት›› ሚና የሌለው መሆኑ ነው፡፡

አሁንም ‹‹ተደባዳቢው›› አካል ማንም ሆነ ምንም ድርጊቱ ትክክል ነው ብዬ አላምንም፡፡ ‹‹ድብደባ›› በሰው ልጅ ላይ ተገቢ አለመሆኑን የማልደግፈው ሰው በመሆኔ ብቻ ነው፡፡ ምናልባት ያነበባቸው ዜናዎች ያስቆጡት ‹‹አካል›› ወይም ‹‹ግለሰብ›. የፈፀመው ከሆነ ለኔ ‹‹አህያውን ፈርቶ ዳውላውን›› ይሆንብኛል፡፡ አሁንም እደግመዋለሁ ፤ ተመስገን በዜና አንባቢነቱ ከሆነ የተደበደበው ነውር ነው – ፖስተኛ ሳይሆን ፖስታውን የፃፈው ነው መጠየቅ ካለበት መጠየቅ ያለበት፡፡ / መደብደብ ያለበት አላልኩም/

እህስ ሌላ ጉዳይ አስደብድቦት ከሆነስ ብለን እንጨምር፤

ዘረፋ የሚፈፅሙ ማጅራት መቺዎች ከሆኑም ‹‹ህግና እግዜር›› መፍትሄ ይሰጡት ዘንድ እመኝለታለሁ፡፡

በማንኛውም ምክንያት ‹‹በቂም ተነሳስቶ›› ተፈፅሞ ከሆነም ‹‹ከድብድብና ስድብ›› ወደ ቅርርብና ፍቅር መምጣት ይቻላል ባይ ነኝ፡፡ በእኔ እምነት ሰውን ከማያግባባው የሚያግባባው ነገር ይበልጣል፡፡ ፍቅር ያሸንፋል!!


ኢትዮጵያን እናድን::

$
0
0

Moving-picture-Ethiopia-flag-flapping-on-pole-with-name-animated-gif

ኢትዮጵያዊ ነን የምንሌ፣ ኢትዮጵያን የምንወድ፣ ኢትዮጵያ ቅድስትና ሏገርና ሏገረ እግዚአብሔር ናት እያሌን ያሇን፣ ዯኑዋ ተራሮቿ ሜዲወቿና ወንዞቿ ከሕዝቧ ተርፎ የአሇምን ሕዝብ ሉመግብ የሚችሌ የተፈጥሮ ፀጋ እንዲሊት የምንመሰክር፣ በስሌጣኔ ወዯሗሊ ብትቀርም ታሪኳ ባህሎና ሏይማኖቷ ድንቅየ ነዉ እያሌን ያሇን በሙለ::
እትብታችን የተቀበረባት ፣ ሳይማር ያስተማረን ወገናችን የሚኖርባት ፣ ሏገራችሁና ሏገራችን እንዱሁም ሕዝቧ በታሪክ አጋጥሟቸው የማያዉቅ ከባድ ፈተና ሊይ ናቸዉ:: ሏገር በቀሌ የሆኑ ከኢትዮጵያ ማሕፀን የተገኙ ግን በበረሏ ሌክፍት ተነድፈው ከራሱ ከሳይጥናኤሌም በሊይ ሳይጥናሌ የሆኑ የዱያብልስ አገሌጋዮች ሏገሯን ከአሇም ካርታ ሇማስፋቅ ሕዝቧን በኢትዮጵያውነት ከታሰረበት እትብት ሇማሊቀቅ ያሊዯረጉት እኩይ ተንኮሌ የሇም እነዚህ የዱያብልስ ተከታዮች እንመራታሇን የሚሎትን ይችን ቅድስት ሏገር ዲር ድንበሯን ሇውጭ ሏገራትና ሇኢትዮጵያ ጠሊቶች አሳሌፈዉ ሰጥተዋሌ ሏገሪቱን ያሇ ባሕር በር አስቀርተዋሌ ያንደን አካባቢ ሕዝብ መሬት ሰርቀዉና ቀምተዉ ሇላሊ አካባቢ ሕዝብ ሰጥተዋሌ አፈር ገፍቶ ቅጠሌ በጥሶ የሚኖርን ሕዝብ ከመሬቱ አፈናቅሇዋሌ በርካታወችን ያሇርሕራሄ በጥይት አረር ቆሌተዉ በአንድ ጉድጓድ ቀብረዋሌ ከሒትሇርም በሊይ ሒትሇር ሆነው ወዯፊት ይወሇዲለ ብሇው ያሰቧቸዉን ትውሌዶች የናታቸውን ማሕፀን በክትባት አድርቀዉ ሌጅ አሌባ አድርገዋቸዋሌ በገዲይ በሽታ(AIDS) የተሇከፉ ታጋያዮቻቸዉን እንጠሊዋሇን ወዯሚለት ሕዝብ ሌከዉ ጤነኞቹን አስሇክፈዋሌ የሏገሪቱን አንጡራ ሀብት ዘርፈዋሌ የሏይማኖት ተቋማትን ተዲፍረዋሌ የሏይማኖት አባቶችን አዋርዯዋሌ ሕዝቡን በሏይማኖትና በጎሳ አናክሰዋሌ ታዱያ ዱያብልስስ ከዚሕ የከፋ ምን ይሰራሌ::
ስሇዚህ ወገኖቸ ይህን ግፍ ማስቆምና ኢትዮጵያን ማዲን አሁን ነው መንገደም ሁሇት ነው አንደ እምቢተኝነት ነዉ እምቢተኝነት ዯግሞ አንድ ሆኖ መቆምን ይጠይቃሌ ነጭ ቀይና ጥቁር ሁነን ከቆምን ግን ይህ ጅብ አንድ ባንድ እየሇያየ ይበሊንና ያሌቅሌናሌ ስሇዚህ መፍትሄዉ አንድ ኢትዮጵያዊ መሌክ ይዘንና እጅ ሇእጅ ተያይዘን ወዯፊት ሇሚመጣ ስሌጣን ሳንስገበገብ ይህን እኩይ ቡድን በተገኘዉ መንገድ ሁለ ተጠቅመን እሚቢተኛነታችን እናሳየዉ ላባ ፈሪ ነዉ ፈሪ ዯግሞ ጨካኝ ነዉ ስሇዚህ ከመጨከኑ በፊት አንድ ሆነን በቃ እንበሇዉ
ሁሇተኛዉ ይች ሏገር ሏገረ እግዚአብሄር ናት ሇዚህም ነዉ ይህ ያሊቋረጠ መከራና ጥፋት ሲዯርስ ሕዝቡም መከራዉን ችል አገሪቱም በቀረዉ አካሎ እስካሁን የቆዩት እግዝአብሔር ኢትዮጵያን አይጥሊትም ፍርደም ትክክሇኛ ነዉ እግዚአብሔር በዙፋኑ ሊይ ሁኖ በቀኙ ስሇኢትዮጵያ በሚሇምኑ ቅደሳን አባቶች በኋሊው ኢትዮጵያን በሚጠብቁ መሊዕክት ታጅቦ ሇኢትዮጵያ ሉፈርድ ይመጣሌ ሇርሱ 10 እና 20 አመት እንዯሰከንዶች ናቸዉ ስሇዚህ ሁሊችንም እንዯየ እምነታችን እጃችን ወዯፈጣሪ ዘርግተን ሇዚች ቅድስት ሏገርና የዋህ ሕዝብ ምህረትን እንዱያመጣሌን ዱያብልስን ከነጭፍሮቹ ከመሬቷ እንዱነቅሌሌን እንሇምነዉ ይሰማናሌ ይፈርድሌንማሌ
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ
ወንድማገኝ ከሰሜን አሜሪካ

የማለዳው ወግ …ተመስገን እላለሁም ፣ አልልምም !

$
0
0

temesgen beyeneበሰላም አውሎ ላሳደረኝ ፈጣሪ ስተኛም ሆነ ስነሳ ” ተመስገን ፈጣሪየ! ” የምትለዋን ምስጋና ከማቅረብ ተቆጥቤ አላውቅም ። ቸርነቱ የማያልቅበት ፈጣሪ አምላኬ አጉድሎብኝ አያውቅም!  ጤና ስጠኝ ስለው ጤናውን ፣ ጥበብ  መላ ላጣሁለት መላ ስጠኝ ስለው መላ ብልሃቱን ፣ ጉልበቴን አበርታው ስለው ብርታቱን ፣ ቅን ልቦና ስጠኝ ስለው ርህራሔውን እና የፈለግኩትን ሁሉ አያጓድልብኝም!  እናም ዘወትር ተመስገን እለዋለሁ !

   ገና ከአልጋየ ሳልነሳ ከአፊ ውስጥ አንድ ቃል ይመላለሳል ፣ ቃሉ ወደ አረፍተ ነገር ሺር በሎ ተቀየረ ! በጨለማ የማያይ አይኔን ወደ ድቅድቁ ጨለማ የመኝታ ክፍል ጣራ አፍጥጦ በምናብ አነበንበዋለሁ … በጀርባየ ተኝቸ ወደ ጣራ ካፈጠጥኩበት ወደ ጎን ግልበጥ እልና  እጆቸን ጭንቅላቴ ስር ወሸቅ አድርጌ  ከአፊ የማወጣውን አረፍተ ነገር ደጋገምኩ  ” ተመስገን ተመስገን ተመስገን አልልም !”  …  እል ይዣለሁ!

የጋዜጠኛ ተመስገን ድብደባ  ሰሞነኛው መነጋገሪያ …

       ለምጀዋለሁና እንደቀሩት ቀናት በአርቡ የሳውዲ የእረፍት ቀን መዳረሻ በድቅድቁ ጨለማ ሌሊት ላይ ነቅቸ የሚነበብ የሚታይ ካለ ዳሰስ ዳሰስ አደረግኩ። የሚሞነጫጨር የማለዳ ወግ መነሻ የሚሆነኝ ጉዳይ ከአንድ የፊስ ቡክ ወዳጀ በኩል በውስጥ መልዕክት ደርሶኛል ። ይህው መልዕክት የደረሰኝ የኢቲቪ ዜና አንባቢ ጋዜጠኛ ተመስገን በየነ ተደበደበ በተባለ ቅጽበት ነበር ። መረጃው ሲሰራጭ እኔም በጅዳ ቆንስል ከድብደባ ያላነሰ ግፍ ተፈጽሞብኝ ነበር ።  በደል እየተፈጸማቸው ፡ እየታመሙና እያበዱ ስላሉ ወገኖቸ ጉዳይ መፍትሔ ፍለጋና ምክክር ስብሰባ “አትሰበሰብም ፣አትመክርም!” ተብየ የታገድኩበት አጋጣሚ ነበርና የሰማሁትም የሆነብኝም አበሳጭቶኝ አዘንኩ ! የቆንስሉን እገዳ መረጃ በጻፈ እጀ በተመስገን ላይ የተቃጣውን ድብደባ የተሰማኝን ስሜት ሳላንዛዛ በተሰራጨው መረጃ ስር አስተያየቴን እንዲህ በማለት አስቀመጥኩ  ” እርምጃው በማንም ይወሰድ በማን ፣ አላስደሰተኝም! ” በማለት …

     ይህ ከሆነ በኋላ በውስጥ መልዕክት መቀበያ ሳጥኔ ብዙ የተቃውሞና ድጋፍ መልዕክት ደረሰኝ!  የለመድኩት ነበርና ሁሉንም በጥንቃቄ እያነበብኩ አለፍኩት ። ከትናነት በስቲያ ከደረሱኝ መካከል ከላይ የጠቀስኩት መልዕክት እንዲህ ይላል” ሰላም ነብዩ በኢባሲ የደረሰብህ በጣም አሳዝኖኛል አሁን የሰማሁት መረጃክ ስለተመስገን መደብ እጅግ አዝኛለው አንተም ሀቅን እንናገር ስላልክ ከኢባሲክ ከተከለከልክ እደተመስገን አንዳያደርጉህ ተጠንቀቅ ” ይላል መልስ የሚያሻው አስተያየት!…  እርግጥ ነው ባለኝ ትርፍ ሰአት መረጃ በማቀበሌ እና ሃሳቤን ባንሸራሸርኩ ፣ ከተቃዋሚ ጽንፈኛ ተብየ እስከ መንግስት ጽንፈኛ ደጋፊዎች የሚሰነዘርብኝ የማስፈራሪያ የዛቻና የ”እንገድልሃለን !” ፉከራ እኔ ለምጀው ባልፍም ብዙዎቹን ያሳስባቸዋል! ከእኒህ ወዳጆቸ መካከል ምክር ለለገሱኝ ወዳጀ ምስጋና ካቀረብኩ በኋላ በሰጠሁት ምላሽ ከጋጠዎጦች ባልተናነሰ እኔንም ሆነ የዜጎች መብት መገፈፍ ያገባናል የምንልን ወገኖች መብት የማያከብሩ ፣ ሰላም የነሱን ፣ መብት ማስከበሩ ቀርቶ የሚገፉን የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ናቸው የሚል መልሴን ሰጠሁ … በዚህ ዙሪያና በተመስገን በምንም ሚዛን ተቀባይነት የሌለው ድብደባ ዙሪያ የማለዳ ወግ አምዴ ልሞነጫጭር ባስብም ድካም የመጻፍ ፍላጎቴን ጎድቶት እንቢ አለኝ !

ዛሬ ሌሊት ….
በድቅድቁ ጨለማ በነቃሁ ሰአት ይህንን እያሰላሰልኩ መረጃዎችን መፈተሽ ይዣለሁ … በኢቲቪ ጋዜጠኛ በተመስገን በየነ ላይ ደረሰበት የተባለውን ድብደባ ተከትሎ የቅርብ ወዳጆቹ ፣ አድናቂዎቹና  የኢቲቪ ጋዜጠኞች የሰጧቸው አስተያየቶች ተበራክተዋል ። ይህን ሁሉ ቃኝቸ ተመልሸ ገደም እንደልኩ እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ አለ  !

በማለዳው ግን ተነሳሁ … እናም ሰሞነኛው ተመስገን አልለቀቀኝም  “ተመስገን አልልም ” እያስባለ ያሚያንሰላስለኝን ሃሳብ ከተጋደምኩበት ቀና ብየ መጻፍ ጀመርኩ  ! ግጥም ሆነ …

ተመስገን ማለቱ ክፉ ነው ባልልም
ስጋቱ ተገፎ ስላላየሁ ዛሬም
ተመስገን ተመስገን ተመስገን አልልም !
የቱ ነው እውነቱ የዝብርቅርቁ አለም ?
ሰው ያለ ሃጢያቱ ከቶ አይወነጀልም ?
ወህኒ አይወረወር አይደበደብም ?
ፍትህን ተነፍጎ ከቶ አይገደለም ?
ለዚህ የሚያስደስት ዛሬ መልስ የለኝም!

ስል በስሜት መነጫጨርሙ … ቀጠልኩ …

ተመስገን ተመስገን ተመስገን ባልልም
ድብደባ ግድያን ፍጹም አልደግፍም !

…  አልኩና አንገቴን አቅንቸ በኩራት ተሞልቸ ተመስገን ተመስገን አልልም ስል የቅርብ ሩቁን ፣ ግራ ቀኙን የነፍስ ማጥፋት እኩይ ምግባር አጠየቅኩ … ምክርም መክሬ ፍላጎት ምኞቴን እንካችሁ አልኩ …

በጠራራ ጸሃይ በሚንቀለቀለው
“ኢትዮጵያዊ ክብሬ” ስላለ ቢከፋው
ቆፍጣናውን መምህር ያን አሰፋ ማሩን ከቶ ማን ገደለው ?
ያንን ጋዜጠኛ ተስፋየ ታደሰን ማነው ያጋደመው?
በምሽት ጨረቃ ድምቅ ፍንትው ባለው ?
ጀኔራል ሃየሎም ማነው የደፈረው ?
በጥይቱ ባሩድ ከእኛ የለያየው ?
ማለዳው ጸሃይ ጸጥ ረጭ ባለው
የደህንነቱን ሰው ክንፈን ገብረ ማን አጠፋው ?
አመት እንኳ ቀርቶ መንፈቅ ባልደፈነው
ወሎ ሰማይ ስር ረግቶ በሚታየው
በምሽት ጨረቃ ሸሁን በጭካኔ ማነው ገዳያቸው?

አልኩና ውጋት ህመም የምለውን ፣ ምክር ዝክር ይሆናል የምለውን ገጣጠምኩትን ! ከሙሉው ግጥም ግጥሜን በቀነጨብኳት ስንኝ ውጌን ልቋጭ …

ችግሩን ለማጥፋት ከሆነ የምናልም
ለድብደባ ፣ እስራት ፣ ለተበራከተው የሰው ልጅ ግድያም
መፍትሄ ፍለጋ ከሆነ ምንሻው እንዳይደጋገም
“ምንድነው ሰበቡ ” ብሎ ማጠየቁ ሳይጠቅም አይቀርም !

ህግ ባለበት ሃገር ግፉ ተበራክቶ ፣ ልዩነቱ ከሰፋ
ችግሩን እንመርምር ያለ መቁረጥ ተስፋ
ፍርድን አናዛባ ፣ ግፉንም አናብዛ ሰውን አናስከፋ
ሃገር አናሰድብ ሰሟን አናስጠፋ
ሰላምን አናውርድ ልዩነቱ ይጥበብ እንድንኖር በተስፋ

ይህን ሳናሟላ ፣ በልዩነት ሰበብ ሰውን አንበድለው
ሰው ከሃገሩ በምድሩ ክብሩን አናሳጣው
መብት በጠየቀ አሸባሪ አንበለው !

ይህን ካደረግ ሰውን ካከበርነው
ማግለልን ካቆምን በዘር በቀለሙ ብሎም በእሳቤው
ያኔ ነው ቀናችን ድብደባ ግድያ የሚጠፋውማ
ያኔ ነው ቀናችን ተመስገን መባያው
እልል የሚባለው ሰለም የሚኖረው!

ጥላቻን አጥፍተን ፣በእርቅ በይቅርታ ደምቀን ስንታይ ነው
ተመስገን  ፣ ተመስገን ፣ ተመስገን የምንለው !

ከእንቅልፍ አንቅቶ ያብተከተከኝን ሙሉ የስንኝ ቋጠሮ በወግ አሰናድቸ እስካቀርበው ለዛሬ የማለዳ ወግ ይህችን  ታክል ካወጋን አይከፋም !  ለእናንተ ለወዳጆቸ መልካም ቀንን ተመኝቸ  አንድየን አመስግኘ እንለያይ ! ፈጣሪ ሆይ አንተን አልፋና ኦሜጋ እናመሰግንሃለን  ! ተመስገን !

ሰላም

ነቢዩ  ሲራክ
ከወይና ደጋው ሳውዲ በአንዷ ከተማ

አስተያየት ለዶ/ር ፍቅሬ ቶሎ(ላ)ሳ፣ ዶ/ር በያን አሶባና ለየደጋፊዎቻቸው

$
0
0

Fikire-tolosa-OLF-and-Ethiopiaእኔ የታሪክም የፖለቲካም ሰው አይደለሁም፡፡ ግን ታሪክ አዋቂ ነን ፖለቲከኛም ነን የሚሉት ሰዎች ለሕዝብ በሚያካፍሏቸው እነሱ ታሪክ ነው ለሚሉት ፅሁፋቸውና አሰትምሮታቸው፣ ምሁራዊ ነው ለሚሉት ትንታኔያቸውና አስተያየታቸው፣ ስኬትን ያመጣል ለሚሉት ንድፈሀሳባቸውና ዕቅዳቸው ለዘመናት የእኔና የመሰሎቼ አእምሮ ለመቀበል እየተቸገረ እራሱ መልሶ እነሱ እኮ ምሁር ናቸው፣ ብዙ ያወቃሉ ለዚህ ትክክል ናቸው በሚል ሲሸነገልና ሲሸነፍ ኖሯል፡፡ ታሪክም (ፅሑፎቹን ማለቴ ነው)፣ፖለቲካም መነሻቸው ጥላቻ በመረዛቸው ፍራቻ ባሸማቀቃቸው አእምሮዎች ተፈብርኮ ታሪክ ወይም ፖለቲካ ከሆነ ምሁርነትን የሚጠይቅ ሆኖ አላያየውም፡፡ በተሻለ እኔ አና እኔን መሰል አንብበንም (ቢያንስ ማንብ እንችላለን) ይሁን የሰማንውን እውነት ወይም ማጣቀሻ ባለው የሀሳብ መነሻ ታሪካዊም ሆኑ ፖለቲካዊ ትንታኔዎችን ብንሰጥ ተፎካካሪ እንደምንሆን ስለደመደምኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚከተለው ጉዳይ ላይ አስተያየት ለመስጠት ሙከራ አደርጋለሁ (ይህ ሙከራ ነው)፡-..ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

 

የደህንነት ከፍተኛ ባለስልጣን በቁጥጥር ስር ዋለ

$
0
0

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ

ህወሓት በሁለት ቡድኖች መከፈሉ ይታወቃል። የደህንነት ሓላፊዎችም እንዲሁ በሁለት የተከፈሉ ናቸው። ሁለቱ የደህንነት ሓላፊዎች አቶ ጌታቸው አሰፋና አቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል ናቸው። በሁለቱም ከፍተኛ ጠብ አለ። አቶ ጌታቸው የነ አርከበ ቡድን ሲሆን አቶ ወልደስላሴ ግን የነ አባይ ወልዱ ሁኖ የወይዘሮ አዜብ መስፍን የቀኝ እጅ ነው።

ሁለቱም የደህንነት ተጠሪዎች በደም የሚፈላለጉ ናቸው። ባለፈው የህወሓት ጉባኤ አቶ ወልደስላሴ ለማእከላዊ ኮሚቴ አባልነት ተጠቁሞ አቶ ጌታቸው ጠንከር ያለ ትችት በማቅረቡ ሳይሳካለት ቀርተዋል። መለስ በህይወት እያለ (በአዜብ ምክር መሰረት) አቶ ጌታቸውን በአቶ ወልደስላሴ ለመተካት አቅዶ ነበር (ሞት ቀደመው እንጂ)።

አቶ ጌታቸው ለመለስ ከማይታዘዙ የህወሓት መሪዎች አንዱና ዋነኛው ነው። ከመለስ ጋር በብዙ ነጥቦች ላይ አይስማሙም፤ የተባለውን ሁሉ የሚሰማ አይደለም። ጠንካራ ነው። ከሙስና የፀዳ የህወሓት ባለስልጣን አቶ ጌታቸው አሰፋ ነው።

የትግራይ ቡድን የአዲስ አበባውን ለማሸነፍ በመለስ ራእይ ስም ከህዝብ መነጠል ችላል። የአዲስ አበባው ደግሞ በሙስና ሰበብ የትግራይ ቡድኑን እያሰረ ይገኛል።

ዛሬ የኢህአዴጉ ሚድያ ‘ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት’ የሃገር ውስጥ የደህንነት መምሪያ ሃላፊው አቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር መዋላቸው ነግሮናል። ጥሩ መጠላለፍ መሆኑ ነው። አቶ ወልደስላሴ የነ አቶ ገብረዋህድ ጓደኛ ነው። አቶ ወልደስላሴ ከታሰረ ወይዘሮ አዜብ መስፍንስ?

ለማንኛውም ቸር ያሰማን!

የኛ ነገር፡ ከኔ ማዕዘን፡- በብርሀኑ ተበሳጨሁ፤ በሰማያዊ ተጽናናሁ፡ በአንድነት ደግሞ ተስፋ አደረግሁ (ከተ/ሚካኤል አበበ)

$
0
0

የኛ ነገር፡ ከኔ ማዕዘን፡ ክፍል 13

በብርሀኑ ተበሳጨሁ፤ በሰማያዊ ተጽናናሁ፡ በአንድነት ደግሞ ተስፋ አደረግሁ

ከተክለ ሚካኤል አበበ

Tekele1-      ይህ ጽሁፍ ዓላማው አድናቆት፡ ትችትና ግብዣ ነው። የአንድነት ምሽት በቶሮንቶ ግብዣ። ከአድናቆትና ከግብዣው በፊት ስለፖለቲካ መሪዎችና ስለፖለቲካ ተንታኞች አትቶ፤ የብርሀኑ ነጋን (ዲባቶ) አቀራረብ ይተቻል። የሰማያዊ ፓርቲን ርምጃ ያደንቃል። የአንድነት ዘመቻን ስለማገዝ ያሳስባል። እንደው ተገጣጥሞ ነው እንጂ፤ አንዱን ለማሞገስ ሌላው መኮሰስም መከሰስም የለበትም። ግን አንዳንዴ ደግሞ፤ በጊዜ ያልተተቸ፤ ይለመዳል። አጉል ልማድ ይሆናል። ሁሉንም ለያይቶ ለመጻፍ ደግሞ፤ ጊዜ የለም። ስለዚህ ባንድ ወንጭፍ ሶስት ወፍ ነው ለመማረክ የምጥረው። ከሀተታ ልጀምር።

የፖለቲካ ተንታኝና የፖለቲካ መሪ

2-      የፖለቲካ መሪ ከፖለቲካ ተንታኝ መለየት አለበት። የፖለቲካ መሪ የፖለቲካ ተንታኝ ሲሆን፤ የጋዜጠኞችንና የፖለቲካ ተንታኞችን/የምሁራንን ስራ ይጋፋል። ያ ብቻም አይደለም። መምራት አቅቶት፤ ወይም መምራት ጠፍቶት፡ በአካልና በስም የፖለቲካ መሪነቱን ወንበር ተቆናጦ፤ በግብር ግን የፖለቲካ ተንታኝነትን ቦታ ይዞ፤ የፖለቲካ መሪነትን ስራ በፖለቲካ ትንታኔ ሊያካክስ ይሞክራል። ያም ብቻ አይደለም፡ የፖለቲካ መሪነት ሚናን ከፖለቲካ ተንታኝ ጋር ያደባለቀ መሪ፤ የያዘውን የፖለቲካ መሪነት ሀላፊነት ከተንታኝነት ሲለሚቀይጠው፤ ትንታኔው ንጹህ አይሆንም። ስለዚህ የፖለቲካ ትንታኔውን መቀበል ይከብዳል። ባይከብድም ትንታኔው ጎዶሎና ወደሁዋላ የሚጎትት፤ ወይንም ወደፊት የማያራምድ ይሆናል። ወይም ትንታኔው ለፖለቲካ ፍጆታ ብቻ የሚደረግ ጥልቅ ያልሆነ ትንታኔ ይሆናል።

3-      ለምሳሌ ብርሀኑ ነጋ ባለፈው የኢሳት ስብሰባ ላይ ያቀረበውን የንግግሩን ገጽ 16 መጨረሻና ገጽ 17 መጀመሪያ ብንመለከት ሀሳቡ ጥልቅ ወይም ሀቀኛ አለመሆኑን በቀላሉ ለመረዳት ይቻላል። http://www.zehabesha.com/amharic/archives/6563 ለዚህም ነው ምሁር ፖለቲከኛ መሆንን ከመረጠ፤ ምሁርነቱን ቀንሶ መሪነቱን እንዲያጠብቅ ግድ ነው የምንለው። ኦባማን ውሰዱ። ኦባማ ሲመረጥ ምሁር ነበር። ከአራት አመት በሁዋላ ግን ምሁርነቱ እየቀነሰ፤ ወደቡሽነት እየተጠጋ መጥቷል። የኦባማ የሶሪያ አቋም፤ ከቡሽ የኢራቅ አቋም ብዙ አይለይም። አሳድን እንበለው ወይም እንብላው እያለ ነው። ኢሳት ባዘጋጀው ስብሰባ ላይ ብርሀኑ ነጋ (ዲባቶ) ያንን መለየት ነው የተሳነው። በፖለቲካ መሪነት መጥቶ (በግንቦት ሰባት ሊቀመንበርነት) የፖለቲካ መሪነቱን ግን ትቶ፤ ምሁር ለመሆን ሞከረ። ተንታኝ። የፖለቲካ ተንታኝ በመሆን የጋዜጠኞችንና የምሁራንን ስራ መሻማት ብቻ ሳይሆን፤ ሁለቱንም ሳይሆን ቀረ። በዚህ ረገድ ጃዋር ይሻላል። እንደተንታኝ በደንብ ይተነትን ነበር። የተንታኝነቱን ሚና ትቶ ባለፈው ሰሞን የራሱን የፖለቲካ አቋም ሲያንጸባርቅም፤ ብዙ ሰዎችን ቢያበሳጭም፤ እቅጩን ነው ያስቀመጠው። ብሬ አድበሰበሰው። በእስር ላይ የሚገኙትም ይሁኑ በነሱ የተተኩትን ከነሱም የቀደሙትን ሙስሊሞች አካሄድና እንቅስቃሴ የሚጠራጠሩ ካሉ፤ ጥርጣሬያቸው በወያኔ ፕሮፓጋንዳ ነው የተፈጠረው ለማለት ይከብዳል። በወያኔ ፕሮፓጋንዳ የማይበገሩም ከተጠራጣሪዎቹ ተርታ ውስጥ አሉበትና።

4-      የዲባቶ ብርሀኑ ነጋ ያልጠራ ትንታኔ የመነጨው፤ ፖለቲካዊ መሪ መሆንና ፖለቲካዊ ምሁር/ተንታኝ መሆንን አጣምሮ ለመሄድ ከመሞከር ነው። የፖለቲካ ተንታኝ የምለው፤ በፖለቲካ ውስጥ በቀጥታ በአድራጊ-ፈጣሪነት ሳይሳተፍ ወይም መሳተፍ ሳይጠበቅበት፤ የአንድን ፖለቲካዊ ስብስብ/ማህበረሰብእ ፖለቲካዊ ሁኔታ እየቃኝ፤ ከአካባቢያዊና አለማቀፋዊ ሁነቶች ጋር እያጣቀሰ፡ የሁነቶቹን ምክንያት የሚያብራራ፤ ሊከሰቱ የሚችሉ ነገሮችን የሚጠቁም፤ አደጋዎችን የሚተነብይ፡ ተመልካችና ተናጋሪ ማለት ነው። የፖለቲካ መሪ የፖለቲካ ተንታኝ ሲሆን፤ አደናጋሪ ነው የሚሆነው። የፖለቲካ መሪዎች የፖለቲካ ተንታኝ መሆን የለባቸውም እያልኩ አይደለም። እኔ የምለው፤ አንደኛ ፖለቲካ መሪዎች የፖለቲካ ትንታኔ ችሎታቸው የሚገለጸው በፖለቲካዊ አመራራቸው በሚወስዱት ፖለቲካዊ እርምጃ ውስጥ መሆን አለበት ነው። ሁለተኛ፡ ፖለቲካን መተንተን የፖለቲካ መሪዎች ዋና የአደባባይ ስራ መሆን የለበትም ነው። እዚያው ድርጅታቸው ውስጥ እንደፍጥርጥራቸው። ይፋዊ ፖለቲካዊ ስራቸው ግን፤ መምራት እንጂ መተንተን አይደለም። አቶ መለስ ከሞቱ በሁዋላ ብቻ ያለውን ሁኔታ እንኳን ብንለመከት ግን፤ የግንቦት ሰባት ሊቀመንበር ብርሀኑ ነጋ፤ ከሲሳይ አጌና ጋር ያደረጋቸውን ቃለምልልሶች ወይንም ያለፈው ሰሞንን የኢሳት መድረክ ጨምሮ፤ በቀረበባቸው መድረኮች ላይ የሚናገራቸወን ስንለመከት አድራጊ የፖለቲካ መሪ ሳይሆን፤ ተንታኝ ጋዜጠኛ ወይንም እዚህ አገር እንደሚሉት ጠቢብ ምስክር ለመሆን ነው የጣረው።

5-      ያ ብቻም አይደለም፤ አሁን በእመ-ብርሀን፤ ሰላሳ ድርጅቶች የኢትዮጵያን እጣፈንታ ከህዝብ ጋር ሊመክሩ በተሰበሰቡበት መድረክ ላይ ለመነሻ የሚሆን የአስር ደቂቃ ንግግር አድርጎ የተቀረውን ሰዓት ለህዝብ ውይይት መተው እንጂ፤ የ55 ደቂቃ ድርሳን ማንበብ ምን የሚፈይደው ነገር አለ? ብርሀኑ ነጋ ባለፉት ሶስት ወራት በኢሳትም ይሁን በተለያዩ መድረኮች ያገኘውን እድልና ሰዓት ስንመለከተው ደግሞ የንግግሩ መርዘም ስህተትነትና አበሳጭነት ይጎላል። ያ ብቻም አይደለም፤ ሶስት ሺህ ምናምን አመት፤ መጀመሪያ በጸሀዩም በጨረቃውም በማምለክ፤ ከዚያ ብሉይን በመቀበል፤ ከዚያ ክርስትናን፤ ከዚያ እስልምናን፤ ከዚያ ካቶሊክን፤ ከዚያ ፕሮቴስታነንስዝምን፤ በመቀበልና በማቻቻል ለኖረች አገር፤ የሊበራሊዝምና ዴሞክራሲ መፍትሄ ለሀይማኖት ነጻነት የሚል የአንድ ሰዓት ስብከት ያስፈልጋታል? ቢቀርብንስ?

6-      በዚህ ኢሳት ባዘጋጀው ስብሰባ ላይ፤ ግንቦት ሰባትን ወክሎ ንግግር ካቀረበው ብርሀኑ ነጋ ይልቅ፤ የሽግግር ምክርቤቱ እጥር ምጥን ባለች ባለአራት ገጽ ወረቀቱ፤ የተሻሉ የሽግግር ሀሳቦችን አቅርቧል። http://etntc.org/ENTC/wp/wp-content/uploads/ESAT-Presentation-0818.pdf። እነሱ የሚመኟት ኢትዮጵያ ምን መምሰል እንዳለበት፤ ሽግግሩ ምን እንደሚመስል፤ የሽግግር ሰነድ የሚያረቅ ኮሚቴ ስለማዋቀራቸው፤ አለማቀፍና አገርአቀፍ የእምቢተኝነት ቡድን ስለማቋቀም፤ ድርጅታቸው ምን እየሰራ እንደሆነ ተናግሯል። ከሽግግር ምክርቤቱ አራት አመት ቀደም ብሎ የተቋቋመው ግንቦት ሰባት ግን ጥምረት ከተቋቋመ ከሶስት አመት በሁዋላ፤ የከማል ገልቹ ኦነግ ከተመለሰ ከሁለት አመት በሁዋላ፤ ገና ስለድርጅቶች አንድነት፤ በጋራ ትግል ወያኔን ስለማስወገድ አጣዳፊነት ይሰብካል። የዛሬ አመት፡ የዛሬ ሁለት አመት፡ የዛሬ ሶስት አመት ከነበርንበት ብዙም ፈቀቅ አላልንም።

7-      ኢሳት ይሄንን ስብሰባ ማዘጋጀቱ ይደነቃል። ይሁን እንጂ፤ የኢሳት አስተዳዳር የሆነው ወዳጄ ነአምን ዘለቀ የዛሬ አመት አካባቢ እንዲህ ያለው ተመሳሳይ ስብሰባ ሲዘጋጅ፤ (ያኔ ስብሰባው የተዘጋጀው በኢሳት ሳይሆን በግንቦት ሰባትና በነኑሮ ደደፎ (ዲባቶ)/ከማል ገልቹ ኦነግ ነበር)፤ እባክህን መሪዎቹ ንግግር ያሳጥሩና ለሰዉ እንዲተነፍስ ግዜ ይስጡት ብዬ አሳስቤው ነበር። ነአምን አንዳንዴ አይሰማም። ወይም ቢሰማም አያደምጥም። እነሆ፤ ባመቱ፤ ሌላ ውድ መድረክ ባከነ። የብርሀኑ ነጋ ጽሁፍ፤ የመጀመሪያው አስራሶስት ገጽ ለዚያ መድረክ አስፈላጊ አልነበረም። ነገር መቁረጥና ማሰጠር፤ እንዲሁም መድረክ ላይና ምድር ላይ የምናቀርበውን መምረጥ አለብን። ያለበለዚያ ትክክለኛና ውጤታማ ሚናችንን መለየት አለብን።

ተስፋ፡ አድናቆትና፤ ግብዣ

8-      መቼም ተቃጥላችሁ አትሙቱ ያለን ፈጣሪ መጽናኛ አያሳጣንም፤ በግንቦት ሰባት ሊቀመንበር አቀራረብ ብንበሳችም፤ አላህ የሚያጽናናን አላሳጣንም። የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ሁኔታ እኛ በምናደርገው ነገር ምንም ቀስቀስ በማይልበት፤ ፖለቲካዊ አየሩ ጸጥ ረጭ ባለበት ሁኔታ ነው፤ የዛሬ ሶስት ወር አካባቢ፤ ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ የተሳካ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ አደረገ። ላለፉት ስምንት አመታት ሰልፍ አይታ ለማታውቀው አዲስ አበባ ሀያ መቶም የሁን ሀያ ሺህ ሰው ያስወጣ ሰልፍ ተከሰተ። ያ ያጽናናል። እነሆ ያኔ በያዙት ቀጠሮ መሰረት፤ ሁለተኛው የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ በመጪው እሁድ ይቀጥላል። መቼም ብዙዎቻችን ፈሪዎችና ሸሺዎች በሆንበት ሁኔታ፤ ጥቂት ዠግኖች አልጠፉምና፤ የሰማያዊ ፓርቲዎች ድፍረትና ቁርጠኝነት የሚያስደንቅ ነው። የህወሀት ኢህአዴግ መንግስት ባለስልጣናት፤ በአዲስ አበባ መስተዳድር በኩል ሰልፉ ህገወጥ ነው ቢሉም፤ የሰማያዊ ፓርቲ መሪዎች ግን ሰልፉ ህጋዊ ነው፤ እንገፋበታለንም እያሉ ነው። የመጪው እሁድ ትልቅ ተጋድሎ ዋዜማ ላይ ነን።

9-      እንዲህ ያለውን ትእይነት ቆሞ መመልከት ብቻ ግን ነውር ነው። መቼም አንዴ ሸሸተን ወጥተናል፤ በወጣንበትም ቢሆን ግን፤ የምንችለውን እንኳን በማድረግ ተዋናይ መሆንም አለብን። የኛ የተቀናቃኙ/ተፎካካሪው/ተቃዋሚው ጎራ፤ በተለይ በውጪ የምንኖረው ተቃዋሚዎች ትልቁ ችግር፤ ማድረግ የምንችለውን እንኳን ማድረግ አለመቻላችን ነው። በሰላማዊም ይሁን ደማዊ መንገድ፤ በአመጽም ይሁን በጸሎት ለሚታገሉት ስንቅና ትጥቅ ማቀበል። ስንቅና ትጥቅ ላለማቀበል ብዙ ምክንያት መደርደር ይቻላል። ምንም ምክንያት ግን አጥጋቢ አይሆንም። ቅዳሜና እሁድ የዱለትና የቁርጥ ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያን ጉዳይ እያብራራ የሚተነትነው፤ የምእራባዊያንን ሴራ የሚመሰጥረው ወዳጄ፤ የኢሳት ዝግጅትን የ20 ብር ትኬት ስሰጠው ፊቱን እንዳጨፈገገው መሆን የለብንም። ለሰማያዊ ፓርቲ ሁለተኛ ሰልፍ መሳካት እንጸልያለን። በጸሎት ብቻ አናበቃም። በግብርም እንከተላለን።

10-   መቼም በየከተማው ብዙ የማይደክማቸው ሰዎች አሉ። እነሆ በመጪው ቅዳሜ ማታ፤ በዚህ በኛ ከተማ ትንሽ ተንፈስ እንላለን። ተሰብስበን ኢህአዴግን ከመዘልዘል ባሻገር፡ የትግሉ በረከት እንጥፍጣፊ ይደርሰን ዘንድ የአንድነት ምሽት ያዘጋጁ አሉ። “የአእላፋት ድምጽ ለነጻነት” የተሰኘውን የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን ዘመቻ በመደገፍ እዚህ ቶሮንቶ ከተማ፤ እንደፈረንጆቹ ዘመን አቆጣጠር፤ ቅዳሜ ኦገስት 31 ማታ ከ6ሰኣት ጀምሮ’፤ 2050 ዳንፎርዝ ጎዳና በሂሩት ሬስቶራንት የቤተሰብ አዳራሽ የእራት ምሽት ተዘጋጅቷል። በሰሀን $ 50 ብቻ። ለጥንዶች $ 60። ለኔቢጤው ደሀ ደግሞ $ 30 ብቻ። ገቢው፤ ከወጪ ምላሽ ለአንድነት ፓርቲ የሚሄድ ነው።

11-   እነሆ፤ በአካል ከግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሀይል ጋር ላንዘምት እንችላለን። በአካል ከሰማያዊ ፓርቲም ጋር አንሰለፍ ይሆናል። ከአንድነት የነጻነት ድምጾች ጋር ለመጮህ ግን አይሳነንም።ለሚጮሁት ጉልበት፤ ለሚሰለፉት ብርታት፤ ለሚዘምቱትም ጽናት ልንለግስ እንችላለን። በያለንበት አካባቢ ያሉትን የፖለቲካ ድርጅቶች እንርዳ። እዚህ ቶሮንቶ ያለን፤ ቅዳሜ ሂሩት ሬስቶራንት ብቅ እንበል። ቅዳሜ እንኩዋን፤ ላሊበላና ብሉናይል፤ ዞብልና ራንዴቩ ይቅሩብን። ቅዳሜ ማታ፤ ሂሩት ጋር እንገናኝ።

እኛው ነን። ከቶሮንቶ። ነሀሴ፡ 2005/2013።

ማኀበረ ቅዱሳን በዌብሳይቱ ላወጣው ርዕሠ አንቀጽ የተሰጠ ምላሽ

$
0
0

እውነት መስካሪ – ከሚኒስታ

mahbere-kidusan-300x168ማቅ፡ ‘‘ ማኅበረ ቅዱሳን ከዚህ ቀደምም ከማንም በፊት በሀገራችን የአክራሪነት ዝንባሌዎች እንዳሉ በማመልከት በኩል ግንባር ቀደም ሚና ተጫውቷል፡፡ “አክራሪዎች” በተለያዩ አካባቢዎች አብያተክርስቲያናትን ሲያቃጥሉ ክርስቲያኖችን ሲያርዱ አካሔዱ መልካም አለመሆኑን በመጠቆም እርምጃ መውሰድ እንደሚገባ በማሳሰብ ሀገራዊ ሓላፊነቱን ለመወጣት ሞክሯል፡፡ የሃይማኖቶች መከባበር በመላው ሀገሪቱ እንዲሰፍን ያለውን ቁርጥ አቋምም አንጸባርቋል፡፡’’

መልስ፦ ለመሆኑ ከዚህ ቀደም በቤተክርስቲያንና በካህናት በምእመናንና በንዋይተ ቅዱሳን ላይ የደረሰውን ውድመት በርግጥ የፈጸመው ክፍል ማን እንደሆነ በምርመራ ተረጋግጦ ነው ‘አክራሪዎች’ ናቸው ብላችሁ ርምጃ እንዲወሰድ የተናገራችሁት? ድርጊቱ የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ለማጥፋት ካልቻለም ለማደከም የተነሳውን በቤተመንግስት ያለው ጸረ-ኢትዮጵያና ጸረ-ኦርቶዶክስ ኃይል እንዳላደረገው ምን ማረጋገጫ አላችሁ? አንዱን ብሔረሰብ ከሌላው ለማጋጨት ከላይ እታች ሲል የኖረና ያልተሳካለት አጥፊ ቡድን ዛሬ ደግሞ አንዱን ኃይማኖት ከሌላው ጋር ለማጋጨት የሚያደርገውን ታላቅ ሴራ እንዲሳካለት የሚያግዝ የእንካ በእንካ የቤት ስራችሁ እንዳልሆነ በምን ማረጋገጥ ይቻላል?

 ሙሉውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

 

ድምፃችን ይሰማ ኢሕአዴግ በጠራው ሰልፍ ላይ በመገኘት አክራሪነትን እንደማይደግፍ በመግለጽ ኢሕአዴግን ሊያሳፍረው ነው

$
0
0

ከድምጻችን ይሰማ

የትኛውንም አይነት አክራሪነት ሙስሊሙ ህብረተሰብ እንደሚያወግዝ በእሁዱ ሰልፍ በአደባባይ ያስመሰክራል!
ጁምአ ነሐሴ 24/2005

‹‹አክራሪነትን ሕገ-መንግስቱ ቢፈቅድ እንኳን አንቀበለውም!›› ኮሚቴዎቻችን

ለዚህች አገር ሰላም እና ደህንነት መንግስትን ጨምሮ ሁሉም ወገን ከአክራሪነት ሊርቅ ይገባዋል!

muslim1አክራሪነት ማለት ድንበር ማለፍ ማለት ነው፡፡ አክራሪነት ዜግነት የለውም፣ በእምነት አይወሰንም፣ በቦታ አይከለልም፣ በሐገር አይለይም፡፡ በግል፣ በህብረት፣ በመንግስት ደረጃ ሊከሰት የሚችል ነው፡፡ አክራሪነትን ከማንም በፊት ያወገዙት ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ) ስለሆኑና የጥፋት አቅጣጫ መሆኑን ስለጠቆሙን አክራሪነትን ለመቃወም ከማንም በፊት ቀድመን የምንገኘው እኛው ነን፡፡ አክራሪነትን የምንቃወመው መሰረታችን ለአክራሪነት የሚመች ስላልሆነ ነው፡፡ ተቻችሎ መኖርም ቋሚ አጀንዳችን ስለሆነ ነው፡፡ ለዚህች አገር በሰላም መኖር ሁሉም ወገን ከሁሉም አይነት አክራሪነት ርቆና እውነተኛ የሰላም ፈላጊ ሆኖ መኖር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው፡፡ ህዝቦች በጋራ በተግባቡበት ህግ በሰላም የመኖር፣ በሃይማኖቶች መካከል መከባበር የአስተምህሮታችን መሰረት ሲሆን በሚሊዮኖች ፊርማ ወክለን በግፍ የታሰሩትን ኮሚቴዎቻችንን ጨምሮ መስዋእትነት የምንከፍልለት ሰላማዊ ትግላችን በኢትዮጵያ የሃይማኖት ነፃነት እና የሃይማኖቶች ተከባብሮ የመኖር ሂደት አካል ነው፡፡ አክራሪነት ማለት ግን ዛሬ ፖለቲከኞች እንደሚጠቀሙት ተለክቶ እንደሚሰፋ ልብስ ሊያጠቁት የሚፈልጉትን አካል ሁሉ በልክ በልኩ አሰፍተው አልብሰው የሚያጠቁበት መቆመሪያ አይደለም፡፡

ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ለሁለት አመታት ስንቃወም የኖርነውም መንግስታዊ ሃይማኖት (አህባሽ) በመንግስት ሙሉ እቅድ እና ትግበራ አማኞችን ለመከፋፈልና የእርስበርስ ፀብ ለመፍጠር ከሌሎች ሃይማኖቶችም ጋር አብሮ የመኖር ገመድን ሊበጥስ ‹‹ከመንግስት የወረደ ነውና ተቀበሉት›› ተብሎ ስለተጫነብን ነው፡፡ መሪዎቻችንም ሆኑ በሺ የሚቆጠሩ ንፁሃን በእስር የሚማምቅቁት ብሎም በርካቶች የሞቱትና የተደበደቡት ‹‹እኔ ከመረጥኩላችሁ ውጭ ትክክለኛ እምነት የለም›› የሚልን አክራሪነት በመቃወም እንጂ በሌላ አይደለም፡፡ መንግስት የእምነት መብት መጠየቃችንን አክራሪት ሲል ፈርጆታል፡፡ ይህ መብት መጠየቅን በአክራሪነት የሚፈርጅ ፖለቲካዊ አክራሪነትን በፅኑ እናወግዛለን፡፡ በሃገራችን ተጨባጭ ፅንፈኛ የፖለቲካ አካሄድ የትክክለኛው አክራሪነት መፈልፈያ መሆኑን እያየን ነው፡፡ በዚህ አክራሪነት ከማንም በላይ የተጠቃነው እኛ ነንና አክራሪነትን በፅኑ እናወግዘዋለን፡፡ ይህንንም ለማሳየት ነው የእሁዱን ሰልፍ የምንሳተፈው፡፡

የነሃሴ 26 ሰልፍ ህዝበ ሙስሊሙ ከሌላ ሃይማኖት ተከታይ ወንድሞቹ ጋር የሚገናኝበት፣ ስለሃገሩ ስላም ያለውን ቀናዒነት የሚያሳይበት መድረክ በመሆኑ ሙስሊሙ ከሌሎች ሃይማኖት ተከታይ ወንድሞቹ ጋር ሰላምታ በመለዋወጥ አድራሻ በመለዋወጥ ጠንካራ አብሮነትን የሚያጠናክርበት ነው፡፡ ትናንት የጥምቀት በዓሉን ታሳቢ በማድረግ የተቃውሞ መርሃግብሩን የከለሰለትና ቦታ ከቀየረለት ህዝበ ክርስቲያን ጋር ነሃሴ 26 በአንድነት ቆሞ አክራሪነትን በጋራ እያወገዘ ሰላማዊነቱን ያስመሰክራል፡፡ በተጨማሪም የነሃሴ 26 የቅዋሜ መድረክ ከሁሉም እምነት ተከታዮች ጋር ያለንን ትስስር የምናጠናክርበትና ሰላማዊ የመብት ጥያቄአችንን ይበልጥ የምናስረዳበት መልካም አጋጣሚ ነው፡፡ ሰልፉን እንደጠራው የሚነገርለት የሃይማኖት ጉባኤ ውስጥ ያሉ የሃይማኖት አባቶች ለዚህች ሃገር እውነተኛ የሰላም አስተማሪና ተጠሪ መሆናቸውን፣ ለችግሮች መፍትሄ በማፈላለግ በመሰለፍ ሃገራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አደራ የምንልበትም ዕለት ነው፡፡

ሰልፉ የሃይማኖቶች ጉባኤ ከሚባለው ተቋም ጋር ህዝብ የሚኖረው የመጀመሪያ የአደባባይ ግንኙነት በመሆኑ የተቋሙን አሰላለፍ በተግባር ለማየት ምቹ አጋጣሚ ነው፡፡ በመሰረቱ የሃይማኖቶች ጉባኤ መንፈሳዊ መሪዎች ያሉበት በመሆኑ ‹‹አክራሪነትን እናወግዛለን›› በሚል መሪ ቃል በጠሩት ሰልፍ የአደባባይ ውንብድና ቢፈፀም በወከላቸው አማኝ እና በተወከሉለት እምነት ላይ ታላቅ ክህደትን መፈፀም ነው የሚሆነው፡፡ መንግስትም ይህንን ሰልፍ ለርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ለማዋል ከተሯሯጠ በሃገሪቱ እምነት የሚጣልበት ነፃ ተቋም ፈፅሞ አለመኖሩን ማስመስከር ሲሆን በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን ደግሞ ያለ እፍረት መደበኛ ተግባሩ እንዳደረገው ለመላው ኢትዮጵያዊ በገሃድ የሚያውጅበት አጋጣሚ ይሆናል፡፡ በዚህ አጋጣሚም መንግስት ሰልፉን ለሃገራዊ መግባባት እንዲያውለው አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡ ዜጎች በሃይማኖታቸው ተከብረው መብት በመጠየቃቸው ሳይሸማቀቁና ሳይበደሉ የሚኖሩባትን ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ትውልድ ለማቆየት መልካም አጋጣሚ በመሆኑ መንግስት እድሉን በአወንታዊ መልኩ ሊጠቀምበት ይገባል እንላለን፡፡

ከዚህ ውጭ ግን ‹‹የሃይማኖቶች ጉባኤ ጠርቶታል›› ለተባለው ሰልፍ ተሳትፎ መንግስት የህዝብን ጓዳ ማስጨነቁ፣ ሰልፉን በማዘጋጀት ብቻ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ በማስፈፀም በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ ገብነቱን በግልፅ እያሳየ ነው፡፡ መንግስት ‹‹አክራሪነትን እዋጋለሁ›› በሚል ሽፋን እምነታችንን ክፉኛ ጣልቃ ገብቶበታል፡፡ አሁን ደግሞ ‹‹አክራሪነትን እናወግዛለን›› በሚል ሽፋን ህዝብን በግዳጅ ጭምር በማስወጣት ይህን ሰልፍ ከሃገራዊ መግባባት ይልቅ ለእኩይ አላማ ሊጠቀምበት አስቦ ከሆነ ተግባሩን በፅኑ እናወግዛለን፡፡ ይህ ተግባር የመንግስት መዋቅር ከዚህ ቀደም ፖለቲካን ሽፋን አድርገው የሃይማኖት እና የቡድን አጀንዳን ለማስፈፀም ለሚሯሯጡ አመራሮች እንደተጋለጠ ሁሉ፤ አሁን ደግሞ በሙሉ መዋቅሩ በሃይማኖት ሽፋን ፖለቲካዊ ቁማር ለመጫወት አስቦ ከሆነ በፅኑ እናወግዘዋለን፡፡

በመሆኑም ይሄን ሽፋን ገልጠን በማውጣትና መንግስት ሊደበቅበት ያሰበበትን ካባ በማውለቅ ‹‹አክራሪነትን አዎ እናወግዛለን!››፣ ‹‹በአክራሪነት ሽፋን ግን በእምነታችን ጣልቃ መግባትንም በተመሳሳይ እናወግዛለን›› ልንል ወደ ሰልፉ እንተማለን፡፡ በሰልፉ ላይ በመገኘት መንግስት ሰልፉን ከተቀመጠለት ስያሜ ውጪ ለህገ ወጥ ተግባሩና ፖለቲካዊ ትርፍ ማጋበዣው መጠቀሚያ እንዳያደርገው እናደርጋለን፡፡ ሃላፊነት በጎደለውና ከልክ ባለፈ ንቀት የሙስሊሙን እምነት ለመበረዝ ሲሞክርና አማኙን በማንገላታት ለመፍጠር የታለመው ሀገራዊ ትርምስ አልሳካ ሲል ዛሬ አሰላለፍን በመቀየር በሃይማኖቶች ሽፋን ህዝብን በህዝብ ላይ ለማነሳሳት የተቀመረ ስሌት ካለ እንደማይሳካ የፊታችን እሁድ በተግባር እናስመሰክራለን፡፡ ይህን ክፉ ራዕይ ዳግም መና ለማስቀረት ዛሬም ከሃገር ወንድምና እህቶቻችን ጋር እምነትና አስተሳሰብ ሳይለየን እጅ ለእጅ በመያያዝ ለዘመናት በገዢዎች ያልተናደውን አንድነታችንን እናጠናክራለን፡፡

የነሃሴ 26 ሰልፍን ስንሳተፍ አክራሪነትን በመቃወም እና አብሮነትና ተቻችሎ መኖርን በተግባር እናሰይበታለን፡፡ ሆኖም አክራሪነትን ከመቃወም ውጭ በሰልፉ ላይ የሚስተናገዱ ማንኛውንም አይነት አፍራሽ መርሃ ግብሮች ካሉ በፅኑ እናወግዛለን፡፡ ሁሌም ደጋግመን ስንገልጸው እንደነበረው ሁሉ የሙስሊሙ ህብረተሰብ ጥያቄም ሆነ እንቅስቃሴ ሰላማዊ፣ አገራዊ እና ህዝባዊ መሆኑን እንዲሁም ይምነት እንጂ የፖለቲካ ጉዳይ አለመሆኑን እና ከመብት እና የፍትህ ጥያቄ ውጭ የተለየ መልክ እና ይዘት እንደሌለው ለሁሉም ኢትዮጵያውያን አሁንም ደግመን ማስረገጥ እንሻለን:: በመሆኑም ሙስሊሙ ኅብረተሰብ በሙሉ ከእነ ቤተሰቡ ነቅሎ በመውጣት በእሁዱ የተቃውሞ መርሐ ግብር ላይ እንዲሳተፍ ጥሪ ተላልፏል፡፡ ሁላችንም እዛው እንገናኛለን፡፡ ለእለቱ ከሚቀመጠው መርሐግብር ክንውን ሳንላቀቀ የተቀመጠውን ብቻ በመፈጸም አክራሪነትን ከሌሎች ኢትዮጵያውን እህቶችና ወንድሞች ጋር በመሆን በተግባር እናወግዛለን፡፡

የነሀሴ 26 መርሐግብር አፈጻጸም በተመለከተ
ጁምአ ነሐሴ 24/2005

በዕለቱ መደበኛውን የሰልፍ መርሃግብር ሙሉ በሙሉ በቋሚነት የምንከተል ሲሆን በተጨማሪ ግን

* ሁሉም የሃይማኖት አባቶች ሰላምን፣ ፍቅርን እና መቻቻልን እንደሚሰብኩ፣ እኩይ ተግባራትን እና አክራሪነትን እንደሚቃወሙና የሰላም እንደራሴዎች እንደሆኑ ለማሳየት እንዲሁም የሃይማኖት አባቶቹ ለወከሉት እምነትና በእምነቱ ስር ላሉ አማኞች ያለንን ክብር ለማሳየት ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት የማናምንበትን ወይም ሞራላችንን የሚነካ ንግግር ቢያደርጉ እንኳ በጥሞና ንግግራቸውን እናደምጣለን፡፡ በምንም መልኩ የሃይማኖት አባቶቹ ንግግር ሲያደርጉ ንግግራቸው እንዲቋረጥ አናደርግም፡፡ ንግግራቸውን እንዳጠናቀቁም የሰላም መገለጫ የሆነ ነጭ ነገር እናውለበልባለን፡፡ ለዚህም መሃረብ፣ ነጭ ወረቀት፣ ሶፍት እና መሰል ቀላል ነገሮችን መጠቀም እንችላለን፡፡

* ህዝብ በይፋ ባወረደው ህገ-ወጥ የቀበሌ ሹመት የመጡ የመጅሊስ ሹመኞች ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት ንግግራቸውን እስኪጨርሱ ያለምንም ድምፅ ሁለቱንም ጆሯችንን በመዳፋችን ደፍነን እንቆያለን፡፡

* ንግግር የሚያደርጉ የመንግስት ባለስልጣናት ካሉ በሚሊዮኖች ፊርማ የወከልናቸው ኮሚቴዎቻችንን በማሰር መላውን መብት ጠያቂ ህዝበ ሙስሊም ያሰሩ መሆናቸውን ለመግለጽና የነጠቁንን መብታችንን በመመለስ ሕዝቡን ከእስራት እንዲፈቱት ለመጠየቅ ንግግራቸውን እስኪጨርሱ ያለምንም ድምፅ ሁለት እጃችንን ወደላይ ከፍ አድርጎ በማንሳትና በማጠላለፍ ምልክት ብቻ እናሳያለን፡፡

ማስታወሻ፡-

- ወደሰልፉ የምንሄደውም ሆነ የምንመለሰው ሌሎች የሰልፉ ተሳታፊዎች በሚሄዱበት ሁኔታ ሲሆን በዋናው መርሐግብር ላይም ሆነ ከዚያ በፊት እና በኋላ ከተጠቀሱት ውጭ ሌላ ምንም አይነት እንቅስቃሴ ማድረግ በጭራሽ የለብንም፡፡


“ትግላችን የህግ የበላይነትን ወደ ማስከበር ተሸጋግሯል!”–ሰማያዊ ፓርቲ

$
0
0

semayawi partyሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ባካሄደው ታላቅ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ለመንግሥት ያቀረብናቸው ጥያቄዎች መልስ ባለማግኘታቸው ለሕዝብ ቃል በገባነው መሠረት በድጋሚ ተቃውሞ ሰልፍ አቅዶ አስፈላጊውን እንቅስቃሴ እያደረገ ነው፡፡ ለዚህም ሥራ መሳካት ለሚመለከተው የመንግሥት አካል ነሐሴ 13 ቀን 2005 ዓ.ም. በደብዳቤ ያሳወቀ ሲሆን፣ መጀመሪያ ባቀረብነው ደብዳቤ ላይ ያልተካተቱ ጉዳዮችን እንድናካትት ነሐሴ 15 ቀን 2005 ዓ.ም. በተፃፈልን ደብዳቤ ተጠይቀን አስፈላጊውን መልስ አሟልተን ነሐሴ 17 ቀን 2005 ዓ.ም. በተፃፈ ደብዳቤ አሳውቀናል፡፡
በአዋጁ በግልፅ እንደተደነገገው ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ህገ መንግሥታዊ መብት እንደሆነና ማንም ሊከለክለን እንደማይችል በማያሻማ መንገድ ተገልጿል፡፡ ሰልፉን የማሳወቁ ዓላማ የጥበቃ አገልግሎትና አንዳንድ አስተዳደራዊ ድጋፎችን ለማግኘት ነው፡፡ በዚህ አሰራር ውስጥ መንግሥት የጥበቃና የቦታ ችግር ካለ ሰልፉን ለሌላ ጊዜና ቦታ እንዲያደርግ ለሚመለከተው አካል ደብዳቤ በደረሰው በ24 ሰዓት ውስጥ በፅሑፍ መልስ ይሰጣል የሚል ድንጋጌ አለ፡፡ ነገር ግን በመንግሥት በኩል ላቀረብነው የመብት ጥያቄ ምላሽ መሰጠት ሲገባው እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ የመንግሥት መዋቅር ሙሉ በሙሉ በመጠቀምና ዜጐችን አስገድዶ ሰልፍ እንዲወጡ በማስፈረም ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ በጠራበት ቀንና ቦታ ሌላ ሰልፍ በተደራቢ በሃይማኖት መቻቻል ስም ህገ መንግሥቱን በመጣስ የሃይማኖት ተቋማትን ለራሱ የድርጅት ፖለቲካ መጠቀሚያና የሰማያዊ ፓርቲን ህጋዊ እንቅስቃሴ ለመግታት እየተጠቀመበት ነው፡፡ ይህ አሰራር እንዲስተካከል መንግሥትን በመግለጫ ብንጠይቅም የተሰጠን ምላሽ ግን በሚያሳዝን ሁኔታ የሀገሪቱን ህገ መንግሥትና የሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብትን ሙሉ በሙሉ በመጣስ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ዲኤታ እንዲሁም ሰልፍ ጠሩ በተባሉ አካላት ግልፅ የሆነና የተቀነባበረ ህገ ወጥ ሴራ ሆኗል፡፡
ስለሆነም በነገው ዕለት ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. የምናደርገው ሰላማዊ ሰልፍ ከዚህ ቀደም ያቀረብናቸው ጥያቄዎቻችን እንዲመለሱ ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረብ ከመሆን አልፎ የህግ የበላይነትን ወደ ማስከበር አድጓል፡፡ በመሆኑም በመንግሥት የሚደረገው ዓይን ባወጣ ሁኔታ ህግን የመጨፍለቅ ተግባር እንዲቆም ለምናደርገው ትግል የኢትዮጵያ ሕዝብና ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ከጐናችን እንዲቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ምንጊዜም የተባበረ የሕዝብ ትግል ያሸንፋል!
ነሐሴ 25 ቀን 2005 ዓ.ም.
አዲስ አበባ

ሽብርተኛው ወያኔ/ኢህአደግ በሀይማኖቶችና በህዝቦች መካከል ግጭት ለመፍጠር የሚያደረገውን እኩይ ሴራ እናወግዛለን! -ENTC

$
0
0

entc-logo-5ባሳለፍናቸው ወራት በኢትዮጵያ የሚገኙ የተቃዋሚ ድርጅቶች እየደረሱባቸው ያሉ አፈናዎችንና እስሮችን በመቋቋም ህዝቡ  ለመብቱ እንዲቆም እያደረጉ ያሉትን የማነቃቃትና የማንቀሳቀስ ስራ፤ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሙስሊሞችም ሳይገድሉ  እየተገደሉ ያለመታከት ከአንድ አመት በላይ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለጥያቄያቸው ምላሽ በመሻት ድምዳቸውን  በማሰማታቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሽግግር ምክርቤት ያለውን አድናቆትና አክብሮት ይገልጻል። እንቅስቃሴዎቹም  የሽግግር ምክርቤት ከሚከተለው የህዝባዊ እምቢተኝነት የትግል ስልት ጋር ተዛማጅ በመሆናቸው ሙሉ ድጋፋችንን መግለጽ  እንወዳለን ።ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

አረመኔው የሕወሐትና የደሕንነት ሹም – (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

$
0
0

weldesilaseየሕወሐት አባልና የአገር ውስጥ ደህንነት ዋና ሃላፊ የነበረው ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል ከያዘው ስልጣን መነሳቱን ምንጮች በመጥቀስ ከሁለት ወር በፊት ዘገባ አቅርበን ነበር። በጭካኔው የሚታወቀውና በሙስና የተነከረው ወ/ስላሴ በሙስና ዘብጥያ ወርዷል። በእስር ቤት በሺህ የሚቆጠሩ ወገኖችን ያሰቃይ የነበረው ወ/ስላሌ ከበረሃ ጀምሮ በርካታ የድርጅቱን ታጋዮች በመረሸን እንደሚታወቅ ባለፈው ዘገባ መገለፁ ይታወሳል። በትግሉ ዘመን የፓርቲው አባለት « ፆታዊ ግንኙነት ስታደርጉ ተገኝታችኋል…» በሚሉና ሌሎች ተልካሻ ምክንያቶች እንዲረሸኑ በበላይ አመራር ውሳኔ የተላለፈባቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ የፓርቲው አባላት (ታጋዮች) ለመግደል ይጣደፉ ከነበሩት መካከል ኢሳያስና ወ/ስላሴ ዋናዎቹ ነበሩ ። አቶ መለስ ሁለቱን አባላት ወሳኝ በሆነው የደህንነት ቢሮ ቁልፍ ስልጣን የሰጧቸው « አድርጉ » የተባሉትን ያለማመንታት ተግባራዊ እንደሚያደርጉ ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ነበር። ወ/ስላሴ ስልጣን በጨበጠ ማግስት በአንድ ቀን አርባ የቢሮው አባላትን ( መኮንኖች ተብለው ነው የሚጠሩት) እንዳባረረ የገለፁት ምንጮቹ፣ በየጊዜው በመቶዎች የሚቆጠሩ አባላትን « ተሃድሶውን አልተቀበላችሁም፣ የቅንጅት ደጋፊዎች ናችሁ..» በሚሉና ሌሎች ምክንያቶች ከማባረር – እስር ቤት እስከመወርወር የደረሰ እርምጃ ሲወስድ ቆይቷል። ከመለስ ጋር በሃሳብ ያለተስማሙ ሁለት ከፍተኛ ባለስልጣናትን በገዛ መኖሪያ ቤታቸው በገመድ በማነቅና በስለት በማረድ የጭካኔ ተግባር ያስፈፀሙት ወ/ስላሴና ኢሳያስ መሆናቸውን ተገልጧል። በግፍ የተገደሉት የመገናኛ ሚ/ሩ አቶ አየነውና የቤተመንግስት የደህንነት ሹም አቶ ዘርኡ ናቸው።
መስከረም 2 ቀን 1996ዓ.ም የኢትኦጵ ጋዜጠኛን ቢሮው በማስጠራት ለሁለት ሰአት ያክል ካስፈራራው በኋላ እንደሚገድሉት ዝቶ አሰናበተው። ጋዜጠኛው በ15 ቀን ውስጥ አቋሙን አስተካክሎ፣ የመረጃ ምንጮቹን አሳልፎ ካልሰጠ እንደሚገደል ነግሮ ያሰናበተው አረመኔው ወ/ስላሴ፣ መስከረም 20 ቀን 1996ዓ፣ም ሰባት የፌደራል ፖሊሶችን በማሰማራት ጋዜጠኛው የግድያ ሙከራ እንዲፈፀምበት አድርጓል። ፖሊሶቹ አካሉን ካጎደሉትና ክፉኛ ከደበደቡት በኋላ ድልድይ ውስጥ ወርውረት እንደሄዱ ይታወቃል። በ1997 እና 98 ዓ.ም በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተወሰደውን ጭፍጨፋ፣ እስርና ድብደባ ከጠ/ሚ/ሩ ትእዛዝ በመቀበል ተፈፃሚ ያደረገና ዋና ተዋናይ የነበረው ወ/ስላሴ፥ ዜጎች ያሰቃይበት ወደነበረው ማእከላዊ እስር ቤት ተወርውሯል።

ርዕስ በምርቃት፤ የማን ሙት አመት? (ስለ ሙስሊም ጉዳይ፤ ስለ አገር ጉዳይ)

$
0
0

muslim and christian
ሁለት ዓመት ሊሞላው እየተንደረደረ ያለው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመብት ንቅናቄ ሂደት በተለያየ ወቅት የተለያዩ ጎላ ብለው የሚታዩ ክስተቶችን እያስተናገደ አሁን ላለበት ደረጃ ደርሷል። እነዚህ ጎላ ያሉ ክስተቶች አንዳንዴ ብቅ የሚሉት ከወደ መንግስት በኩል ሲሆን እኔም ጨረፍ አድርጌ ለማለፍ የምሞክረው ይህንኑ ከመንግስት በኩል ጎላ ብሎ ብቅ ያለውን ወቅታዊ ዘመቻ ነው። እንደሚታወቀው ይህ የሙስሊሙ የመብት ጥያቄ ወደ መጀመሪያ አካባቢ ከመንግስት እውቅና ተነፍጎት ለጥቂት ጊዜ ከቆየ በኃላ የህዝቡን አካሄድ “ሸውደን” ማለፍ አንችላለን በሚል ድምዳሜ “ሰላማዊና ህገመንግስታዊ ” ስለመሆኑ ከመንግስት በኩል ይፋዊ ያልሆነ (በቃልና በደብዳቤ) ሙገሳ “ተችሮለት” ከመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴው ጋር “ንግግር” ተጀመረ። በቅፅበትም መንግስት በይፋ እውቅና ያልተሰጣቸውን እነኚሁ ጥያቄዎች “ትክክለኛ” መሆናቸውንና “በአጥጋቢ ሁኔታ መመለሳቸውን” በይፋ በመገናኛ ብዙሃን ማስለፍለፍ ጀመረ። በተጓዳኝም ሰላማዊ የነበሩት የኮሚቴው አባላት ባንድ ጀንበር የ “አሸባሪነት ” ካባ ተደረበላቸው። ይሄ ኮሚቴውን “የመነጠል” ዘመቻ እስከ ቀትር አላስጉዝ ሲል: ወዲያው ጥያቄው “የጥቂት አክራሪዎች” ስለመሆኑና “ሰፊው ሙስሊም” ሕብረተሰብ ከመንግስት ጋር ስለምሆኑ ሰፊና ረጅም ዘመቻ ተከፈተ። ሙስሊሙን የመከፋፈል መሆኑ ነው። በዚህም ወቅት አንዳንድ ግልሰቦችን የተለያየ ቆብ አስለብሰው በቴሌቪዥን ላይ እያመጡ ስለ መንግስት ጥሩነት አስለፈፉ። እነዚሁን ግለሰቦች አንዴ ኮፍያ አንዴ ጥምጣም አንዴ ጋቢ አንዳንዴም አረንጉአዴ ነገር እያለበሱ: ሲላቸው “አንዳንድ ያዲሳባ ወይንም የምንትስ አካባቢ” ነዋሪዎች: ሲላቸው ደግሞ “የታወቁ የሃይማኖት ምሁራን” ወይንም ያገር ሽማግሌ: ገፋ ሲልም “የአህሉ ሱና ወልጀመአ” አባላት እያሉ ያቀርቧቸው ነበር። “የአህሉ ሱና ወልጀመአ” ማለት መንግስት “አህባሽ” የምትለዋን መገለጫ ለመደበቅ የዘየዳት የሽወዳ ቃል መሆኗ ነው። የሚገርመው አነዚሁኑ በጣት የሚቆጠሩ ግለሰቦችን በስብሰባውም በቃለመጠይቁም በውይይቱም ባውደጥናቱም “በግንዛቤ ማስጨበጫውም” በወዘተውም በሁሉም ላይ ተናጋሪ መሆናቸው ነው። አንዳንዶች ምነው መንግስታችን ስንት ድራማ መስራት እየቻለ ለዚህ የሚሆኑ ሌሎች ሰዎችን መጨመር አቃተው? ይሉ ነበር። (በቅርብ ግዜ እንደወጡ ዘገባዎች ከሆነ መንግስት ሰላዮቹን እስራኤል ድረስ እየላከ በእስልምና ትምህርት አሰልጥኗል።)
ይሄው ረጅም ግዜ የወሰደው የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ትንሽ እንኳ ጠብ ብሎ መንግስት የፈልገውን የመከፋፈል ሴራ ሊያሳካ ይቅርና ይብሱኑ ሙስሊሙ ኅ/ሰብ “ይሄ ነው ወይ መንግስት?” “እነዚህ ናቸው ወይ ያገር መሪዎች?” እያለ ይጠይቅ ገባ። በተያያዥነትም ተጠናክሮ የቀጠለው የፖሊስ ወከባ፣ አይን ያወጣ ዝርፊያ (በተለይም የኪስ ገንዘብ ነጠቃና የሞባይል ስልኮች ቅሚያ) እና ቅጥ ያጣው መረን የለቀቀው የደህንነቶች ዛቻና ማስፈራሪያ (intimidation) በሥራና በንንግድ ቦታ እየመጡ ማሸማቀቅ፣ በየቢሮው እየገቡ የፌስቡክ አካውንቶችን አስገድዶ ማስከፈት በተለይም ባንድ ወቅት በሰፊው ሲያኪያሄዱት የነበረው የሌሊት ቤት ሰበራና ዝርፊያ ከሁሉም በላይ ተጠናክሮ የቀጠለው እስር፣ ቶርችና ግዳያ: ሙስሊሙን ኅ/ሰብ ከማበሳጨትና ከማሳዘን አልፎ: የመብት ትግል ሙቀትን ከሩቁ የሚሸሹ፣ ከመንግስት ጋር “መነካካትን” የማይፈልጉ፣ እንዲሁም መጀምሪያ አካባቢ በመንግስት ተደናብረው የነበሩ ዜጎችን እስከነአካቴው ጥርግርግ ብለው ትግሉን እንዲቀላቀሉ አድርጓቸዋል። የመንግስት ምኞት በዚህ ዘመቻ የትግሉን “አንቀሳቃሾች ማደንና” በጊዜ ሂደት መረቡን በጣጥሶ ትግሉን ማዳከምና ማክሰም ቢሆንም የሆነው ግን ተቃራኒው ነበር። ከአመት በፊት መሪዎችን በማሰር ትግሉን ለማዳፈን ያሰበው መንግስት በድጋሚ በዚህ ዘመቻውም ሊሳካለት አልቻለም። መንግስት በሙስሊሞች ላይ ሲያሴር የነበረውን “የመከፋፈል” አጀንዳ አንዳልተሳካለት ያረጋገጠው ክስተት የታየው በቅርቡ በተከበረው የኢድ በዓል ላይ ያካሄደው የጅምላ (indiscriminate) ጭፍጨፋ ሲሆን ሴት፣ ሕፃን፣ አሮጊት፣ ሽማግሌ ሳይል ለስለላና ለጥቆማ የላካቸውን ጀሌዎቹን ሳይቀር ያለርህራሄ የደበደበት ሂደት ነበር።
መንግስት በሙስሊሞች ላይ ያለውን ካርታ ተጫውቶ ጨርሷል፣፣ አሁን የሚቀረውን የመጨረሻ ካርድ በክርስቲያኑ ሕብረተሰብ ላይ መዟል። የወያኔ ውሸት ፍርድ ቤት እንኩአን ለድራማ አይመችም ብሎ ውድቅ ያደረገውን “ጥያቄው እስላማዊ መንግስት መመስረት ነው” የምትለዋ ቧልት፣ “በጠቅላይ ሚንስትርነት ማዕረግ ተመድቤ እየሰራሁ ነው” በሚሉት ግለሰብ (አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ) አጋፋሪነት አንደገና ተቀስቅሳ ክርስቲያኑን ለማስበርገግ ሰፊና የተቀናጀ ዘመቻ ተጀምሯል። (እዚህ ጋር የኬንያው ፕሬዝደንት ለረመዳን ሙስሊም ዜጎቻቸውን እንኩዋን አደረሳችሁ ለማለት አብረው የረምዳን አፍጥር መዓድ ሲቋደሱ፣ የኛው “መሪ” ግን ለኢድ በዓል በዋልታ በኩል ያስተላለፉት መልክት “ዋ! እንገላለን” አይነት መሆኑ ከኬንያ ጋር ያለንን ርቀት ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ወደጉዳያችን፣) ይህ እጅግ አደገኛ የወያኔ “የክፉ ቀን” ካርድ በብዙዎች ዘንድ አንዲህ በቀላሉ ይመዘዛል የሚል ግምት አልነበረም። እነዚህ ጨቋኞች የፈልጉትን ለማግኘት አገሪቱ ዶግ አመድ ብትሆን ደንታም እንደሌላቸው በግልፅ የታየበት ወቅት ላይ ደርሰናል።ይህ ዘመቻ በአገር ውስጥና በውጭ ኢትዮጵያውያን በብዛት በሚገኙበት አካባቢ በስፋት አንዲካሄድ የታቀደ ሲሆን፣ በአገር ውስጥ አንደነ ሪፖርተር፣ አዲስ አድማስ፣ ሰንደቅ አና ሌሎችም ጋዜጦች ልክ አንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ በቅንጅት እየሰሩበት ነው። እንደምታስታውሱት አንዴ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በውጭ አገር ዕረፍት ላይ ናቸው ሲላቸውም ቤተመንግስት ውስጥ እያገገሙ ነው፣ ክብደት የቀነሱት በአዲሱ ዳይት ነው፣ ነገ አዲሳባ ሊገቡ ነው ወዘተ በማለት ህዝብን እንዲያደናግሩ የተሰጣቸውን ኃላፊነት ሲወጡ የነበሩ ጋዜጦች፣ አሁን ደግሞ አዲሱን ተልዕኮዋቸውን ለመወጣት አየሰሩ ይገኛሉ።

muslimየዛሬ ዓመት አካባቢ“እነ አሕመዲን ጀማል ይቅርታ ጠየቁ” በሚል ርዕስ “አሕመዲን ጀማልን ጨምሮ በእስር በሚገኙት ሥምንት አባላት ፊርማ ደብዳቤው ለምክር ቤቱ እንደደረሰም ምንጮች ተናግረዋል፡፡” በማለት ስለታሰሩት የሙስሊም ኮሚቴ አባላት ሕዝቡን ለማደናገር የሞከረው አዲስ አድማስ ዘንድሮ ደግሞ “በ22 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ያስተዳደረ ሙስሊም የለም” የሚል መፈክር ሙስሊሞች ይዘው ወጡ ብሎናል። ጥያቄው “የስልጣን” ለማስመሰል ሆን ተብላ የተጨመረች መሆኗ ነው። ሪፖርተር ደግሞ በበኩሉ በ”ክቡር ሚኒስትር” አፃፃፍ ዘይቤ አይነት (satire) “የሙስሊሞች ፖለቲካዊ ጥያቄዎችና ፖለቲካዊ መፍትሔዎች” በሚል ርዕስ የፈበረክውን ልብወለድ “እውነት” አስመስሎ ለማቅረብ ሞክሯል። ይህንን የወያኔ ዘመቻ ልዩ የሚያደርገው በውጭ ያሉ የስርዓቱ ደጋፊና በመንግስት በጀት የሚደግፉ ድረገፆችና ሬድዮችን አቀናጅቶ መንቀሳቀሱ ነው። እነዚህ ድረገፆችና ሬዲዮ ፕሮግራሞች ከፍተኛና ሀልፊነት የጎደለው የስም ማጉደፍ ዘመቻ በሙስሊሙ ወገናችን ላይ የከፈቱ ሲሆን ግልፅ የሆነ የሙስሊም ጥላቻ “በአክራሪ” ስም ይሰበክባቸዋል። በተለይም በየድረገፆቹ አስተያየት መስጫ አምዶች ላይ ስማቸውን ቀያይረው እስላምና ሙስሊሞች ከምድረገፅ መጥፋት አንዳለባቸው በግልፅ ይወተውታሉ።ክርስቲያኑን ሕብረተሰብ ልትታረድ ነው እያሉ ከማስፈራራት አልፈው ትግራይ ኦንላይን በተባለው ድረገፅ “ተነስ” ተደራጅ ሳትቀደም ቅደም የሚል ግልፅ የጥፋት ጥሪ አስተላልፈዋል። ባንድ ወቅት የሙስሊሙን ጥያቄ ከዓባይ ግድብ፣ ግብፅና ናይል ፖለቲካ ጋር ለማሳሳብ ሌት ተቀን ሲታትሩ የነበሩ አሁን ፊታቸውን በቀጥታ ሙስልሙን ወደማጥቃት አዙረዋል። በተለያዩ የኢንተርኔት ገፆች የተገኙ ከእውነት የራቁና ምንም ሳይንሳዊ መስረት የሌላቸው “ጥናታዊ ፅሁፎች” በአማርኛ እየተተረጎሙ በድምፅና በፅሁፍ ያቀርባሉ። በተለያየ ወቅት “ከፓልቶክ” መድረክ ላይ “ተቀዱ” የተባሉ በማን አንደተንገሩ የማይታወቁ አፀያፊ ንግግሮች ከባዕድ አገር ከተፈፀሙ ቪድዮች ጋር እየተቀናበሩ ክርስቲያኑን የማስበርገግና ፍትሃዊ የሆነውን የሙስሊሙን ጥያቄ የማጠልሸት ዘመቻ ላይ ውለዋል። በአሜሪካን አገር በአክራሪ ነጭ ዘረኞች በሚመሩ ቤተክርስቲያናት አማካይነት በቢሊዮን ዶላር የሚቆጠር ገንዘብ ፈሶባቸው የሙስሊም ጥላቻን ለማስፋፋት የሚሰሩ የተለያዩ ፅሁፎችና የሚዲያ ውጤቶች ላገራችን ሕዝብ እየተፈተፈቱ ያቀርባሉ።
ወያኔን ወደዚህ አደገኛ ውሳኔ ካደረሱት ነገሮች መካከል ሁለቱን አሁን መጥቀስ እፈልጋለሁ። አንደኛው የሙስሊሙን ሰላማዊ የመብት ጥያቄ ማዳፈን እንደማይችል ድምዳሜ ላይ በመድረሱ ሲሆን፣ እንቅስቃሴውን ለመምታት ሰላምዊ ሂደቱ መደናቀፍ አለበት ብሎም ያምናል። እስካሁን ድረስ እልህ አስጨራሽ ትንኮሳዎችን ተቋቁሞ ሰላማዊነቱን ማስጠበቅ የቻለውን የሙስሊሞች ትግል ወደ አገራዊ ብጥብጥና የሃይማኖት ግጭት ካመራ ፣ መንግስት “ሰላምን” በማስጠበቅ ሰበብ የገደለውን ገድሎ (የፖለቲካ ተቃዋሚውንም ጭምር) የቀረውን ሰጥ ለጥ ብሎ እንዲገዛ ማድረግ እችላለሁ፣ ፣ በተጨማሪም ከምዕራባውያን “ለፀረሽብር ትግሉ” የማይነጥፍ ገንዘብና መሳሪያ አገኛለሁ። እንዲሁም ማንኛውም የፍትህ የዲሞክራሲና የእኩልነት ጥያቄዎች እስከወዲያኛው ተዳፍነው ይቀራሉ ከሚል ቅዥት ሲሆን። ሁለተኛውና ተያያዥ የሆነው ምክንያት ደግሞ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ይህን የሙስሊሙን ሰላማዊ ትግል የመኮረጅና የመደግፍ አዝማሚያ መንግስትን በጣም ስጋት ላይ ስለጣለው ነው። ለዚህም ነው የመንግስት ባለስልጣናት ከሀይለማርያም ደሳለኝ እስከ ሽመልስ (ሼምየለሽ) ከማል ስለ “ፓርቲዎችና አክራሪዎች ጋብቻ” የሚያወሩት። ይህ ክርስቲያኑን የማስበርገግና የማነሳሳት ዘመቻ ፓርቲዎች ላይ ተፅዕኖ የማሰደርና ከሙስሊም ወገናቸው እንዲርቁና በተቃራኒውም እንዲቆሙ ግልፅ የሆኑ ጥሪዎች የተካተቱበት ነው። ይህው በክርስቲያኑ ላይ የተከፈትው የማስፈራራት ዘመቻ በሙስሊሞች ላይ የሚያርፈውን የግፍ ዱላ በማጠናከር የሚታገዝ ነው። ሙስሊሙን በበለጠ የማጥቃት አጠቃልይ ዘመቻ በቅርቡ የተጀመር ሲሆን እስርና ግድያውን ለማስፋፋት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ከራሱ ከመንግስት ባለስጣናት አፍ እየተነገር ነው።አቶ ኃይለ ማርያም “ትግስታችን አልቁዋል” ሲሉ አቶ በረከት ደግሞ ህዝቡ መንግስት ቦንብና መትረየስ አንዳለው አያውቅ ይመስል “መንግስት ኃይል አለው ጉልበት አለው” ብለዋል። (አይዝዎ አቶ በረከት ሳር ሳይሆን የሰው ሕይወት አጭዳችሁ ለዚህ መብቃታችሁ; እሱንም ለማስጠበቅ ባደባባይ መቶዎችን እንደረሸናችሁ ህዝቡ ጠንቅቆ ያውቃል።) ሙስሊሙ በግፍ ብዛት ሲማረርና የወገን ያለህ ሲል ክርስቲያኑ ደግሞ ሙስሊም ወገኑን ይብሱኑ እንዲፈራው፣እንዲጠላው ጭራሹንም “ይገባቸዋል” እንዲልና አመቺ ሆኖ ሲገኝም በጥቃቱ እንዲተባበር ለማድረግ ያለመ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ነው። ይህ የመንግስት እቅድ ከተሳካ በክርስቲያኑና ሙስሊሙ ሕብረተሰብ መካከል ሊፈጠር የሚችለው የሃሳብ ልዩነትና ተቃርኖ ምን አይነት አስቃቂ ጉዳት ባገራችን ላይ ሊያደርስ እንደሚችል መገመት አያዳግትም። ስለዚህም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ይህንን መሰሪ ተንኮል ላገሪቱና ለራሱ ደህንነት ሲል በአንድነት በመቆም ማክሸፍ መቻል አለበት።
ምርቃት
የማን ሙት ዓመት? የማን ራእይ?

ሰሞኑን የመንግሥትና ደጋፊ ሚዲያዎችን ያጨናነቀው የታላቁ መሪ ሙት ዓመት ዝክር ነበር። ይህ ወደ ወር አካባቢ የፈጀው ሽርጉድ የመንግስትንና የህዝብ የስራ ሰዓትን ከመሻማት አልፎ የዕለት ተለት እንቅስቃሴዎችን አስተጓግሎ እንዲሁም ጥቂት የቀሩ ራዕዮችን ለአቶ መለስ አስረክቦ ቀዝቀዝ እያለ ያለ ይመስላል። እኔ አንዳንዴ ሳስበው ያለ መለስ ራእይ ያገራችን ግብርና ኢንዱስትሪ ትምህርት ጤና ሙዚቃ ጥበብ ሚሊተሪ አንደው ሁሉ ነገራችን የት ይሆን አንደነበር ሳስብ “ይዘገንነኛል”፣ በምድር ሳሉ ያላየናቸው “ራዕዮች” ወደዚያኛው ከሄዱ በኋላ መዥጎድጎዳቸውም አንዲሁ ። እድሜ ለሳቸው (ፅ ፅ! ይቅርታ ሞተዋል ለካ? ለነገሩ አንድ ግለስብ በቴሌቪዥን ቀርቦ ከገድላቸው አንዱ የሆነውን ” አህሉ ሱና ወልጀመአ ማህበር ያቋቋሙልን” ብሎ ሲያሞግስ “ገነት” መግባታቸውን መስክሮልናል።) አዎን እድሜ ለሳቸው ያገሪቱን ወታደራዊ ሃያል አሽመድምደው “ለጠላት” ካገለጧት በኋላ፣ ለምን ዝግጅት አልነበረም? ተብለው ሲጠየቁ፣ ያው እንደተለምደው በቃላት አክሮባት ጥበባቸው ፣ “በቴክኒክ ዝግጁ ባንሆንም በታክቲክ ግን የተሻለ አቅም ፈጥረናል” ሲያብራሩም “ደካማ ወታደርና የዛገ ታንክ ቢኖረንም ለዚያ ይወጣ የነበረውን ለልማት በማዋልችን የተሻልን ነን” አሉንና 80 000 ወጣት ዜጎችን አስጨርሰው በብዙ ቢሊዮን ዶላር የሚቆጠር ያገር ገንዘብና ሀብት አስባከኑ። ለጦርነቱ ከወጣው አጅግ ባነሰ ገንዘብና ያለምንም ሊባል በሚችል የሰው ይህወት ጠንካራ መከላከያ ቀድሞውኑ ቢኖር ኖሮ ያሁሉ ሕልቆመሳፍርት ሕይወትና ንብረት ባልተማገደ ነበር። ይህንን ለማወቅ ላቅምአዳም/ሔዋን መድረስ ብቻ በቂ ነበር። እንግዲህ እኒህ ጠቅላይ ነበሩ የወታደራዊ መሃንዲስ ባለራእይነት የተሸለሙት። እሺ ይሁን ግድ የለም፣ ግን የጋሽ ዘበርጋን ራእይ (ምኞት) ለጠቅላዩ ሲሰጥብኝ ግን አኔ በቃ! ብያለሁ።
ነገሩ አንዲህ ነው፣ ያደኩበት ሰፈር የማገዶ እንጨት በሸክም የሚያመጡ አቶ ዘበርጋ የሚባሉ ሰው ነበሩ፣ አፈሩ ይቅለላቸውና። ናም ያዲሳባ ደን እየተመንጠረ የሳቸውም ጉዞ አየራቀ መጣ። ከእድሚያቸው መግፋት ጋር በቀን ሁለቴ መሄድ እያቃታቸው መጣ። ያኔ ጋሽ ዘበርጋ ተመኙ በጣም ተመኙ ሃስብና ራዕያቸው ሁሉ የሰፈራችን ሜዳና ጋራ በደን ለመሸፈን፣(የዛሬን አይርገውና ያኔ ብዙ ክፍት ቦታና ሜዳ ነበር በየሰፈሩ) አሳቸው ወደጫካ ከሚሄዱ ጫካውን ወደራሳቸው የማምጣት “ራእይን ሰንቁ”። ብዙዎች በድህነታቸውና ባለመማራቸው የሚንቋቸው ጋሽ ዘቤክስ፣ ለብቻቸው ከቀበሌ ከፍተኛ እየተመላለሱ፣ ጠማሞቹን የቀበሌ ሹማምንት አሳምነው ራእያቸውን አሳኩ። ሜዳውን ሁሉ አስፈቅደው ችግኝ በችግኝ አደረጉት። እኛም በልጅ ልባችን እየረገምናቸው የሰፈራችንን ሜዳ ለችግኝ አስረክበን ኳስ ለመጫወት ሩቅ መሄድ ጀመርን። እናም ጠቅላዩ በሞቱ ባመቱ የጋሽ ዘቤ ራእይ እንዲሁ ለሌላ ሲሰጥ የኛ ሰፈር ልጆች ዝም ብለን አናይም! አራት ነጥብ። እኔ ምለው? ጠቅላዩ “ሞቱ” ከተባለ ጀምሮ በየሚዲያው በየቢሮው በየሰብሰባው በየመንገዱ በየወረዳ በኤምባሲዎች ጭምር ፎቶዋቸና ራእያቸው፣ እንዲሁመ የግብርና የኢንዱስትሪ የትምህርት የጤና የሙዚቃ የስነጥበብ የሚሊተሪ እንደው የሁሉም መሃንዲስ ተደርገው እየቀረቡ፣ አሁን “በቁም” ያሉት ሚኒስትር አንድም ቦታ ወይ ስማቸው ወይ ፎቶዋቸው ወይ “ራአያቸው” ሳይነሳ ዓመቱ ሲከበር፣ አሁንም እኔ ምለው የማን ሙት ዓመት ነው “አያከበርን” ያለነው? ማን ነው አንደሙት ስሙ የተርሳው? ማንንስ ነው አንደ ሕያው በየቀኑ የሚወሳው? ኧረ ለመሆኑ በየትኛው አገር ነው ያለው ተረስቶ የሞተው የሚነሳው? ህወሓት በሚመራው።
ሰላሙ ነኝ ቸር ያሰማን!

የአባይ ቦንድ ሽያጭ በጉተምበርግ ከሸፈ፤ ድብድብ ተነሳ (Video)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የኢሕአዴግ በየሃገሩ እየጠራው የነበረው የአባይ ቦንድ ሽያጭ በመክሸፍ ላይ ይገኛል። በየከተማው ስብሰባው እየተበጠበጠ በመበተን ላይም ነው። ባለፈው ሳምንት በሚኒሶታ የአባይ ቦንድ ሽያጭ ሳይጀመር የተበተነ ሲሆን በዚህ ሳምንት ደግሞ በጉተምበርግ ኢትዮጵያውያን የአባይን ቦንድ ሽያጭ አክሽፈዋል። የቦንድ ሽያጩ በተጠራበት አዳራሽ በመግባት በተነሳው ተቃውሞ ድብድብ ተነስቶ የነበረ ሲሆን ሕዝቡ ወንበሮችን አንስቶ ወርውሯል። ሕዝቡ ስብሰባውን ከተቆጣጠረውና የኢሕ አዴግ ተወካዮችን ከአዳራሹ ካባረረ በኋላ “ኢትዮጵያ ሀገራችን…” እያለ ሲዘምር ይታያል። ቪድዮውን ይመልከቱ።

የፌደራል ፖሊስ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ደበደበ፣ ተቃውሞ ሰልፉን አደናቀፈ

$
0
0

ከርእየ- ሁለንተና ከአዲስ አበባ
semayawi partyዛሬ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ. ም ሠማያዊ ፓርቲ በጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ገዥው ፓርቲ ለማደናቀፍ ከፍተኛ ውዥንብር፣ ድብደባና ሁከት ፈፀመ፡፡ ከ3 ወር በፊት ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ. ም ባደረገው የተቃውሞ ሰልፍ፡- ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፣ የሀይማኖት ተወካዮች፣ በግፍ የታሰሩ ዜጎች ባስቸኳይ እንዲፈቱ በስብሰባው ያሳወቀ ሲሆን ምላሽ ባለማግኘቱ ነው ሰልፍ የጠራው፡፡
ይሁንና ገዥው ፓርቲ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሚል መልምሎ ባስቀመጣቸው ካድሬዎቹ አማካኝነት የተቃውሞውን ስብሰባ ያደናቀፈ ሲሆን በ25/12/05 ዓ. ም ምሽት ወታደሮቹን ልኮ በቢሮው ውስጥ የነበሩትን አመራሮችና ደጋፊዎችን ደብድቧል፡፡ አቶ ማርቆስን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ክፉኛ ተደብደበው በ5 እስር ቤቶች ከፋፍሎ ካሰረ በኋላ ከምሽቱ 5፡00 ፈቷቸዋል፡፡ ኢንጅነር ይልቃልም ታስረው ተፈተዋል፡፡ ዛሬ ጠዋት 12፡ 00 ጀምሮ በጽ/ ቤቱ ከፍተኛ ቅስቀሳ የነበረ ሲሆን ወታደሮች በህገ ወጥ ገብተው በማስቆም ፖስተሮችን በመቅደድ፣ ጀኔሬተሮችን በመቀማት፣ ከፅ/ ቤታቸው እንዲወጡ አድርገዋል፡፡
በአንጻሩ በሀይማኖት ተቋማት ስም የጠራው ስብሰባ፡- እድሮች፣ የቀበሌ ነዋሪዎች፣ የቀጠና ካድሬዎች፣ በአነስተኛና ጥቃቅን ያደራጃቸው፣….በሎንችና፣ በአዜብ ቀንዶ፣ በአሮጌ አውቶቡሶች በመጓጓዝ መስቀል አደባባይ ከተገኙ በኋላ ያለምንም ተልእኮ ተበትነዋል፡፡ አብዛኞቹ በእግራቸው ተመልሰዋል፡፡ አላማው የሰማያዊ ፓርቲን የተቃውሞ ሰልፍ ማደናቀፍ ብቻ ነበር፡፡
ይህ የገዥው ፓርቲ ግፍ በዜግች ላይ ከፍተኛ ቁጣና እምቅ እልህ አንደሚፈጥር ታውቋል፡፡

በዛሬው ሰልፍ ላይ ከወጡት መካከል ከ200 በላይ ሙስሊሞች ታሰሩ

$
0
0

Muslim Etiopia 1

Muslim Etiopia 2

Muslim Etiopia 3

Muslim Etiopia 4

Muslim Etiopia 5(ዘ-ሐበሻ) ኢሕአዴግ በሃይማኖቶች ጉባኤ ስም ሽብርተኝነትንና አክራሪነትን ለመቃወም የጠራው ሰልፍ ላይ ፖሊስ ሙስሊሙን ብቻ እየመረጠ ማሰሩን ድምፃችን ይሰማ በፎቶ ግራፍ ጭምር ባወጣው መረጃ አስታወቀ። “ኢሕአዴግ በጠራው ሰልፍ ላይ እንዲገኝ በየወረዳው አውቶቡስ የተዘጋጁ መሆኑ ሲታወቅ አውቶብሶችን ደልድለው ሰውን ያስገቡት የወረዳ ሀላፊዎች ናቸው፡፡ የአውቶብሶቹ ወጪዎች የተሸፈነውና ስምሪት የተደረገው በመንግስት ሲሆን የሰልፉ አዘጋጅ የተባለው የአዲስ አበባ የሃይማኖቶች ጉባኤ የሚባል “አሻንጉሊት” እንዳልታየ ድምጻችን ይሰማ ገልጿል። ኢሕአዴግ በዛሬው ሰልፍ 1 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ወጣልኝ ቢልም አብዛኛው ሰልፈኛ ከድምጻችን ይሰማ የመጡ ናቸው።

በተለይ በመጨረሻው ሰዓት ላይ ድምጻችን ይሰማ ኢሕአዴግ በጠራው ሰልፍ ላይ ተገኝቼ “እኔም አክራሪነትን እንደምቃወም እገልጻለሁ” ባለው መሠረት በርከት ያሉ ሙስሊሞች ወደ መስቀል አደባባይ የተመሙ ቢሆንም ከመንገድ ላይ ፌደራል ፖሊሶች በመቆም ሙስሊሞቹን እየመረጡ ወደ ሰልፍ እንዳይሄዱ ሲያደርጉ እንደእዋሉ የአይን እማኞች ገልጸዋል። ከፖሊስ ተርፈው በመስቀል አደባባይ የተገኙት ሙስሞች ደግሞ ተቃውሟቸውን ለመግለጽ እጃቸውን ወደ ጆሯቸው ባስጠጉ ቁጥር የደህንነትና የፖሊስ አካላት ለምን እጃችሁን አስጠጋችሁ እያሉ ውክቢያ ሲፈጽሙ ነበርና “ለምን ወደዚህ ሰልፍ መጣችሁ?፡ በሚል ሲያዋክቧቸው እንደዋሉ ተዘግቧል። ፖሊሶቹ ስም እየጠየቁ የሙስሊም ስም ያለውን ይመልሱ እንደነበርም ከተገኙት መረጃዎች ለማቀቅ ተችሏል።

በመስቀል አደባባይ ከተገኙት ሙስሊሞች ውስጥ ቁጥራቸው ወደ ከ200 ባልይ የሚሆኑትን ፖሊስ ይዞ ያሰረ ሲሆን ሰልፉ እስኪጠናቀቅ ድረስ በኢግዚብሽን ማዕክል አስሯቸው ከቆየ በኋላ በአውቶቡስ ወዳልታወቅ ሥፍራ እንደወሰዳቸው የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ዘ-ሐበሻ ጉዳዩን ለማጣራት ባደረገችው ሙከራ እስካሁን እነዚህ ሙስሊሞች ያሉበት ያልታወቀ ሲሆን ምናልባትም “ሽብር እና ሁከት ለመፍጠር” በሚል መንግስት አንድ ድራማ በመሥራት ክስ ሊመሰርትባቸው እንደሚችል ታዛቢዎች ይናገራሉ።

ዛሬ ኢሕአዴግ በጠራው ሰልፍ ላይ በመገኘት “የትኛውንም አይነት አክራሪነት እንደማንቀበልና እንደምናወግዝ ዛሬ በድጋሚ በተግባር አሳይተናል” ብሏል ድምጻችን ይሰማ ከሰልፉ መጠናቀቅ በኋላ።

በሌላ በኩል ከሕወሓት የንግድ ድርጅቶች ውስጥ አንዱ የሆነው ራድዮ ፋና የዛሬውን ሰልፍ በማስመልከት ያቀረበው ዘገባን ለግንዛቤ እንዲረዳችሁ በሚል እዚህ አምጥተነዋል።

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች አክራሪነትንና ሽብርተኝነትን በመቃወም አደባባይ ወጡ

አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 26 ፣ 2005 (ኤፍ. ቢ. ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በአስሩም ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች አክራሪነትና አሸባሪነትን በመቃወም ዛሬ በመስቀል አደባባይ ሰለማዊ ሰልፍ አካሄዱ።

ሰለማዊ ሰልፉን የጠራው የአዲስ አበባ ከተማ የሃይማኖትች ጉባኤ ጽህፈት ቤት ሲሆን ፥ ለዛሬ ማለዳ በተጠራው ሰለፍ ላይ ቁጥሩ ከአንድ ሚለየን የሚልቅ ሕዝብ በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ተሳተፏል።

የማለዳው ዝናብና ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ ሳይበግረው ከአዲስ አበባ ከተማ ሁሉም አቅጣጫዎች በመትመም መስቀል አደባባይ የተገኙ ነዋሪዎች “ ሕገ መንግስታችን በአክራሪዎችና ደጋፊዎቻቸው አይናድም ” ፣ “ አክራሪነት ቻው ቻው ” ፣ “በኪራይ ሰብሳቢዎች ስር የተጠለሉ አክራሪዎችን አንሻም” ፣ “የምንፈልገው ሰላምና ሰለም ብቻ ነው ” ፣ “ መንግስት በአክራሪዎችና አሸባሪዎች ላይ አስፈላጊውን እርርምጃ ይውሰድልን ” ፣ ” የፀረ ሽብርተኝነት ህጉን እንደግፋለን ” የሚሉና ሌሎች በርከት ያሉ መፈክሮችን አሰምተዋል።

ከአዲስ አበባ ከተማ የሃይማኖትች ጉባኤ ጽህፈት ቤት የተወከሉ የክርስትናና የእስልምና ሃይማኖቶች አመራሮች ለሰልፈኞቹ ባሰሙት ንግግር ነዋሪዎቹ የጽህፈት ቤቱን ጥሪ አክብረው በመገኘታቸው አመስግነው ሰልፉ ኢትዮጵያ የምትታወቅበት መቻቻል አንድናትና እኩልነት በድጋሚ የተረጋገጠበት መሆኑን አመልክተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አቶ ዲሪባ ኩማም ባሰሙት ንግግር መንግስት የነዋሪዎችን ጥያቄ በማክበር በአሸባሪዎችና አክራሪዎች ላይ ተገቢውን ህጋዊ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን ጠቁመዋል።

የሰላማዊ ሰልፉ ተሳፊዎች በሰልፉ ጠሪዎችና በክብር እንግዶች የተላለፉ መልዕክቶች ከሰሙ በኋላ የኢትዮጵያን ህዝብ መዝሙር በመዘመር ወደየመጡበት ተመልሰዋል።


ዴሞክራሲ በተግባር: ‘ሰላማዊ ሰልፍ መከልከል!’

$
0
0

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ

ዛሬ እሁድ ነሓሴ 26, 2005 ዓም ሰማያዊ ፓርቲ (ና ሌሎች ድርጅቶች) በአዲስ አበባ ከተማ ሰለማዊ ሰልፍ መጥራቱ ሰምተን ነበር። በሕገ መንግስታችን መሰረት ዜጎች ወይ ድርጅቶች ሰለማዊ ሰልፍ ለማድረግ ሲፈልጉ የአከባቢው አስተዳደር ማሳወቅ (ከተቻለም ማስፈቀድ) ይጠበቅባቸዋል። ሰለማዊ ሰልፍ ማድረግ ግን ሕገመንግስታዊ መብታቸው ነው።

የሰማያዊ ፓርቲ የሰልፍ ጥሪ ተከትሎ መንግስት በሀይማኖታዊ ጉዳዮች ዙርያ በተመሳሳይ ቀን የሆነ ሰልፍ ነገር ዘመቻ መጥራቱ ተሰማ። በ አንድ ከተማ በተመሳሳይ ቀን ሁለት ተቃራኒ ሰልፎች ስለመካሄዳቸው ስናብሰለስል መንግስት ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ ለማድረግ እንደማይፈቀድለትና ካደረገ እርምጃ ሊወሰድበት እንደሚችል ትናንት ከወጣ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን መግለጫ መረዳት ይቻላል።

ሰለማዊ ሰልፍ (የተለየ ሁኔታ ካላጋጠመ በቀር) በመንግስት አዋጅ ወይ በተቋሞች መግለጫ ሊከለከል አይችልም፤ ምክንያቱም የዜጎች መብት መሆኑ በሕገ መንግስቱ ተቀምጧል። ሕገመንግስት ደግሞ የሁሉም ሕጎች የበላይ ነው።

መንግስት የተቃዋሚ ሰልፉ ከለከለው (ቢያንስ በፖሊስ መግለጫ)። ራሱ መንግስት የጠራው ሰልፍ ግን ይካሄዳል ማለት ነው። ‘እኔ ስልጣኑ ስላለኝ ሰልፍ መጥራት እችላለሁ፤ እናንተ ዜጎች ግን አትችሉም ‘ እያለን ነው። ዴሞክራሲ በተግባር እንዲህ ነው። የኢትዮጵያ ህገ መንግስት አንቀፅ 30፣ “ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሳሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ፤ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነፃነትና፤ አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡” ብሎ ይደነግጋል።

blue party……………..

መንግስት ፍቃድ መከልከሉ የሀገራችን ሕገመንግስት የጣሰ ነው። መንግስት የራሱን ሕገመንግስት በራሱ ከጣሰ ዜጎች መንግስት የጣሰውን ሕገመንግስት እንዲያከብሩ እንዴት ማስገደድ ይቻለዋል? ዜጎች ብቻ ሕገመንግስቱ ቢያከብሩ እንዴት ዉጤት ማምጣት ይቻላል? በዴሞክራሲያዊ ሀገር ሕገመንግስት የበላይ ሕግ ነው፤ በመንግስትም በዜጎችም መከበር አለበት። ሕገመንግስቱን በመጣስ ኢህኣዴግ የሚመራው የኢትዮዽያ መንግስት ከሕግ በላይ እየሆነ ነው። መንግስት ሕግን በሚጥስበት ሀገር ዴሞክራሲ አለ ማለት አይቻልም። ዴሞክራሲ ከሌለ የኢትዮዽያ መንግስት ‘አምባገነን ነው’ ብንል እንዴት ስሕተት ሊሆን ይችላል?

መንግስት አምባገነን ከሆነ ዜጎች ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚገነቡበት አጋጣሚ ለመፍጠር ብንቀሰቅስ ኃጥያት ይሆናል? መሪዎቻችን ለስልጣን ሲታገሉ ለዴሞክራሲ ግንባታ ብንታገል መልካም አይደለምን? ሰለማዊ ሰልፍ ማድረግ ህዝቦች ሓሳባቸውንና ያላቸው ቅሬታ (በመንግስት ይሁን በሌላ) የሚገልፁበት መድረክ እስከሆነ ድረስ የዴሞክራሲያዊ አሰራር መገለጫ ይሆናል ማለት ነው።

ሰለማዊ ሰልፍ ማድረግ የዴሞክራሲ መገለጫ ከሆነ ታድያ ለምን ሰለማዊ ሰልፍ እንፈራለን? ሰለማዊ ሰልፍ ባለመፍቀድ የህዝብን ብሶት ያቃልላል ያለው ማነው? ህዝብን ማፈን የህዝብን ቅሬታ እንዲጨምር እንደሚያደርግና ህዝቡ ሌላ አማራጭ (ሰለማዊ ያልሆነ መንገድ) ተጠቅሞ ፀረ መንግስት ሊነሳ እንደሚችል ኢህኣዴጎች ከደርግ አገዛዝ ትምህርት አለመቅሰማቸው ግርም ይለኛል። ሰለማዊ መንገድ መዝጋት የሃይል ወይ የዓመፅ መንገድ መክፈት ማለት ነው።

(ኢሕአዴግ በጠራው ሰልፍ ላይ የተገኘ አንድ ሙስሊም በፖሊስ ተይዞ ሲዋከብ)

(ኢሕአዴግ በጠራው ሰልፍ ላይ የተገኘ አንድ ሙስሊም በፖሊስ ተይዞ ሲዋከብ)

እኛ የምንፈልገው ግን የዓመፅ መንገድ ሳይሆን ሰለማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲኖር ነው። ኢትዮዽያ በሃይል ስልጣን የመያዝ የብዙ ዓመት ልምድ አላት። እስካሁን ድረስ የኢትዮዽያ ገዢዎች ስልጣን የያዙት በሃይል ነው። ባለስልጣናቱ (ሰዎቹ) ይቀያየሩ እንደሆኑ እንጂ ፖለቲካዊ አገዛዛቸው ተመሳሳይ ነው፤ ስልታቸው ጭቆና ነው። የሚገለገሉበት ስልጣን ከህዝብ ተውሰው የያዙት ሳይሆን በጠመንጃ አፈሙዝ የነጠቁት ነው፤ ለዚህም ነው ለስልጣናቸው እንጂ ለህዝብ ነፃነት ግድ የሌላቸው።

ሰለማዊ ሰልፍ የምንፈራበት አንድ ምክንያት ሊኖር ይችላል። ይሄም ‘ሰለማዊ ሰልፉ’ እንደስሙ ‘ሰለማዊ’ ላይሆን ይችላል። መፍትሔው ግን ቀላል ነው። በሕገ መንግስቱ የተቀመጠ ‘ሰለማዊ ሰልፍ’ ነው። ሰዎቹም የጠሩት ‘ሰለማዊ ሰልፍ’ ነው። ፍቃድ የተጠየቀው ‘ለሰለማዊ ሰልፍ’ ነው። መንግስት ይሄንን ፍቃድ መስጠት ነበረበት። ሰልፉ ሰለማዊ መሆኑ ቀርቶ የዓመፅ መንፍስ ከታየበት ‘ሕገ ውጥ ሰልፍ’ እየሆነ ነው ማለት ነው። በዚህ ግዜ መንግስት ‘ሕገመንግስቱን ለማስከበር’ ጣልቃ ሊገባ ይችላል። ‘ሕገ ወጥ ድርጊት’ የፈፀመ አካል ካለ ወደ ሕግ ቀርቦ በሕግ ይፈረዳል። (የሕግ የበላይነት ይከበራል)።

ገና ለገና ‘ዓመፅ ሊቀሰቅሱ ይችላሉ’ በሚል ስጋት (ይህን ያልኩበት ምክንያት መንግስት ዓመፅ ፈርቶ ካልሆነ በቀር ሰለማዊ ሰልፍ የማይፈቅድበት አሳማኝ ምክንያት ስላልመጣልኝ ነው) ሰለማዊ ሰልፍ መከልከል የዜጎች መብት መጣስ ስለሆነ አግባብነት የለውም። ባጭሩ መንግስት በሕገወጥ ተግባር ተሰማርተዋል ማለት ነው።

ሰለማዊ ሰልፍ መጥራት የመብት ጥያቄ እንጂ የአቋም ጉዳይ አይደለም።

ዓፈና ዓመፅን ይወልዳል።

የደህንነት ኃይሎች ጋዜጠኞችን ማዋከብና ማስፈራራት አጠናክረው ቀጥለዋል

$
0
0

ከበትረ ያዕቆብ

Fnote23ለረጅም ጊዜ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ አዘጋጅ ሆኖ ያገለገለዉና የጋዜጣዉ ህትመት ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ የኢቦኒ መፅሔት ዋና አዘጋጅ ሆኖ በመስራት ላይ የሚገኘዉ ጋዜጠኛና ብሎገር ብስራት ወልደ ሚካኤል ሰሞኑን በ4 የደህንነት ኃይሎች ታግቶ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እንደተፈፀመበት ተናገረ ፡፡ ድርጊቱ የተፈፀመዉ ባሳለፍነዉ ሰኞ (ነሐሴ 20 – 2005ዓ.ም) ከምሽቱ 2፡35 ላይ ከስራ ወደ ቤቱ በጉዞ ላይ እያለ ነበር፡፡ብስራት ወልደ ሚካኤል እንደገለፀዉ ግለሰቦቹ ለ50 ደቂቃ ያህል ያገቱት ሲሆን ፤ ከአሁን በኋላ በየትኛውም ጋዜጣ ፣ መፅሔትም እንዲሆም ብሎግ ላይ ብትፅፍ በህይወትህ ላይ ፈርደህ ነዉ ሲሉ ዝተዉበታል፡፡ በመጨረሻም በጥፊ መተዉታል፡፡ ብስራት እንደገለፀዉ ከሰዎቹ መካከል አንዱ ሽጉጡን እየደጋገመ በማሳየት ሊያስፈራራዉ ሙከራ ያደረገ ሲሆን ፤ ሌላኛዉ ደግሞ እንዳይንቀሳቀስ ሴንጢ በሆዱ ላይ ደግኖበት ነበር፡፡ ጋዜጠኛ ብስራት አያይዞም “አቶ መለስ ዜናዊ አለዉ ከተባለዉ 3 ቢሊዮን ዶላር እና ልጁ ከታማችበት 5 ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም የፀረ ሽብርተኝነት ህጉን በሚመለከት የፃፋኳቸዉ ፅሑፎች እንዳናደዷቸውና እንዳበሳጯቸው በንግግራቸው ይጠቃቅሱልኝ ነበር” ሲል ተናግሯል፡፡

“ይህን የጋዜጠኝነት ሙያየ ወድጄና ፈልጌ በመማር የገባሁበት እንጂ ተገድጄና ተመድቤበት የምሰራው አይደለም ፤ ከዚህም ሙያ ልወጣ አልችልም ” የሚል ምላሽ ሰጠኋቸዉ ሲል የተናገረዉ ጋዜጠኛ ብስራት ፤ አያይዞም ፀያፍ ስድብ እንደሰደቡትና ከወላጅ አባቱ ጋር በተያያዘ የተናገሩት አሳዛኝ ነገር እንደነበረ ጠቁሟል፡፡ አያይዞም “ከግለሰቦቹ መካከል አንዱን ልደታ ፍርድ ቤት በተለይም በሽብርተኝነት የተከሰሱትን የእነ አንዱዓለምንና እስክንድርን ጉዳይ ልዘግብ ስሄድ ሁሌም እዚያ የማላጣው ሰዉ ነበር” ብሏል፡፡

“ይህንን ሁሉ ወዲያው ሳሪስ ለሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ሄጄ ያሳወቅሁ ሲሆን ፤ ያኔ ተረኛ መርማሪ ፖሊስ የነበረው ኮንስታብል ጥላሁን ታዴ የተባለ ሰዉ ያንተ ጉዳይ ከበድ ስለሚል የጣቢያው ዋና ኢንስፔክተር አበበ አያሌው ሲመጣ ጠዋት ንገረው አለኝ፡፡ በሰዓቱ የሚተባበረኝ ፖሊስ ቢኖር ግን የገቡበትን አቅጣጫ ስላየሁ አጋቾቹን እናገኛቸው ነበር ፤ ግን በሰዓቱ ለሚቀጥለዉ ቀን ከመቅጠር በቀር የተባበረኝ አልነበረም፡፡” በማለት ጋዜጠኛ ብስራት ተናግሯል፡፡ አያይዞም “በነጋታው ማክሰኞ ጠዋት ነሐሴ 21 ቀን ዋና ኢንስፔክተር አበበን ለማናገር ወደ ጣቢያው ብሄድም አሁን የሉም ፣ ለስብሰባ ወጥተዋል ተብዬ ከሰዓት እንድመለስ ተነገረኝ፡፡ ከሰዓትም ስሄድ ተመሳሳይ መልስ ከተሰጠኝ በኋላ ለረቡዕ ነሐሴ 22 ቀን ጣዋት እንድሄድ ተነገረኝ፡፡” ሲል የገጠመዉን ዉጣ ዉረድ አስረድቷል፡፡

እንደሚታወቀዉ ሰሞኑን እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት በጋዜጠኞች ላይ መጠነ ሰፊ ዛቻና ማስፈራሪያ እየፈፀመ ይገኛል፡፡

Art: በሕይወትም በሕልፈቱም እያነጋገረ ያለው ደራሲ ስብሐት ገ/እግዚአብሔር

$
0
0

ከብርሃኑ ዓለሙ

በቅርቡ ከ25 በላይ በሆኑ ፀሐፊዎች፣ ገጣሚዎችና ሰዓሊዎች ስለ ስብሐት ያላቸውን የነፍስ ወከፍ ልቡሰ ጥላ አንድ ላይ አጣምረው መንጉለዋል፡፡ መንጎላቸው ዳጎስ ያለና ባለ 278 መጽሐፍ ተገላግሏል፡፡ ስለ ስብሐት ትናንትም፣ ዛሬም፣ ነገም ይፃፋል፡፡ በሁለት ጎራ በጅር በጅር ሆኖ በብዕር መፋለሙ፣ በመድረክ መከራከሩ ይቀጥላል፡፡ ምክንያቱም ስብሐት አወዛጋቢና አከራካሪ ደራሲ ነውና፡፡
ክርክሩ “መልክአ ስብሐት” የሚል ሥያሜ በተሰጠው መድበልም ታይቷል፡፡ “ሰለሜ ሰለሜ” እንደተሰኘው የአገራችን የደቡብ ጭፈራ ተያይዘው መስመር ያበጁ የደራሲው አድናቂዎችና «አምላኪዎች» በአንድ ወገን፣ «ቤተ ክርስቲያን እንደገባች ውሻ» የሚጠየፉት ደግሞ በሌላ ወገን የብዕር ሙግታቸውን አፋፍመዋል፡፡ የንግግር፣ የመፃፍ፣ ሃሳብን በነፃነት ያለምንም ከልካይ መግለፅ ከዚህ እንደ ምሣሌ መውሰድ ይቻላል፡፡
Sebhat-Gebregziabher
ዓለማየሁ ገላጋይ፣ የኢትዮጵያ ዘመናዊ ልቦለድ ከስብሐት ይጀምራል የሚለው ሃሳቡን እጅግ ከሚቃወሙት ኢትዮጵያውያን መካከል አንዱ ነኝ፡፡ በሃሳብ ልዩነት መፍጠር የሥነ ጽሑፍም በሉት የጥበብ አንዱ መገለጫ፣ ከፍ ሲልም ውበት ነው ማለት ይቻላል፡፡ ዓለማየሁ ገላጋይ ሳያውቀኝ ሳላውቀው እንዲሁ በደምሳሳው ብቻ “አምባ ገነን ” ይመስለኝ ነበር፡፡ ልክ እንደ ኤፍ ኤም አዲስ 97.1ዱ የ“ርዕዮት” ፕሮግራም አዘጋጁ ቴዎድሮስ፡፡ ዓለማየሁ በዚህ መድበል ስመለከተው ግን “ተሳስቻለሁ ማለት ነው?” ብዬ ራሴን ጠየቅኩ፡፡ ዝርዝር ባህርዩን ለማወቅ የዓለማየሁ “ማንዋ” መጠየቄ አይቀርም፡፡
አንዳንድ የአገራችን ጋዜጠኞች ይገርሙኛል፡፡ እነሱ ልክ ነው ብለው ያመኑበትን ሃሳብ የሚቃወም ሲያጋጥማቸው ዱላ ከማንሳት አይመለሱም፡፡ ስለ ዴሞክራሲ አስፈላጊነት እያወሩ፣ ነገር ግን ሰው ተቃራኒ ሃሳብ ሰጠ ብለው ይወነጅላሉ፡፡ ዴሞክራሲ መጀመሪያ ነገር ከራስ ይጀምራል፡፡ ከሚስት/ከባል፣ ከልጅ፣ከጎረቤት ወዘተ እኔ የባለቤቴን የመናገር ወይም አስተያየት የመስጠት መብት የምፃረር ከሆነ እንዴት አድርጌ ነው የሌላውን መብት የምጠብቀው? በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ መፃፍና ብዙ መነጋገር ይቻላል፡፡ አሁን ግን ወደ ጀመርኩት ርዕሰ ጉዳይ መመለስ ግድ ይለኛል፡፡
“ስብሐት ገብረእግዚአብሔርን ከሌላ ማዕዘን” የሚለው የሚካኤል ሽፈራሁ(ው?) መጣጥፍ በጥሩ ሁኔታ ጊዜ ተሰጥቶና ታስቦበት የተሠራ በመሆኑ ሳላደንቅ ባልፍ ኅሊናዬ ይታዘበኛል፡፡ ይሁን እንጂ ሚካኤል ያነሳቸው ነጥቦች ሙሉ በሙሉ ልክ ናቸው ማለቴ አይደለም፡፡ ሚካኤል ያየበት መንገድ የግሉ አተያይ(አንግል) ነውና አስተያየቱን አከብራለሁ፡፡
ብዙዎቹን ፀሃፊዎች በጅምላ መፈረጁ ከባድ ቢሆንም፣ አንዳንዶቹ ግን ሌሎች ያሉትን መነሻ በማድረግ የፃፏቸው፤ ያው የተለመደ የመወዳደስ፣ የመካካብ፣ ወይም በሌላ አገላለጽ የጓደኝነት ስሜት የሚታይባቸው ናቸው፡፡ በርዕስ ከፋፍዬ መተቸትና መተንተን እችላለሁ፡፡ ነገር ግን ይሄ የጋዜጣ ገጽ እንጂ የመጽሔት ያህል እንኳ ነፃነት የሚሰጥ ስላልሆነ በዚያ መሠረት አልሄድኩበትም፡፡
ስብሐት፣ በኢትዮጵያ ረዥምና አጭር ልቦለድ ታሪክ ውስጥ ሁነኛ ሥፍራ የያዘ ትልቅ ደራሲ መሆኑን ማስተባበል አይቻልም፡፡ ስብሐት በቋንቋ ውበቱ፣ በአፃፃፍ ስልቱ፣ በጭብጥ አመራረጡ፣ በገፀ ባህሪያት አሳሳሉ፣ ከመቀመጫዬ ተነስቼ “ዱስቱር” እለዋለሁ፡፡ የስብሐት፦ “አምስት ስድስት ሰባት” አጭር ልቦለድ፣ በኢትዮጵያ አጭር ልቦለድ ታሪክ “ማስተር” ነው ብዬ ባሞካሸው አይበዛበትም፡፡ እነ “እቴ እሜቴ”፣“እኔ ደጀኔ”፣“ሞትና አጋፋሪ እንደሻው”፣”አምስት ስድስት ሰባት” የአጭር ልቦለድ መመዘኛን ከሟሟላታቸው በተጨማሪ ለማስተማሪያ የሚሆኑ ታሪኮች ናቸው፡፡
ስብሐት፣ ከሌሎች ደራስያን የሚለይባቸው ብዙ ባህሪያት አሉት፡፡ አንደኛው፣ ከአብዛኛው ሰው በሃሳብ የማይስማማውን አካፋን አካፋ በማለት ልማዱ የተነሣ ነው፡፡ ስብሐት፣ የመሰለውን እንደመሰለው እንደወረደ ይጽፋል፤እንደወረደ ይናገራል፡፡ በተለይም በወሲብ ዙሪያ ያለው አቋሙ ለብዙዎቹ ኢትዮጵያውያን (በድብቅ ተወልደን በድብቅ እንደግ ለሚሉት) መራራ እውነት ነው፡፡ የወሲብ ርዕስ እንዲህ እንደወረደ መፃፍ “ብልግና ነው” ብለው ፈርጀው ያበቁት፣ ዓይንህን ለአፈር ይሉታል፡፡ ሌሎቹ ደግሞ በሚያጨሰው እፀ ፋሪስ ምክንያት እጅግ ይኮንኑታል፡፡ ደግሞ ሌሎቹ፣ ትውልድን አበላሽቷል (አኮላሽቷል) ብለው ይከሱታል፡፡ “ኲሉ አመክሩ አጽንኡ ወ ዘሰናየ” ተብሎ በተቀኘበት አገር ይህን ያህል ማማረር ግን ተገቢ ነው ወይ? የሚለውን ጥያቄ አንስቼ ባልፍ ደስ ይለኛል፡፡
የስብሐት መንገድ ለየት ያለ ነው፡፡ እኔ ብመኘውም ወይም እሆናለሁ ብዬ ፀጉሬን ባንጨባርር፣ ጺሜን ባጎፍር፣ ለመፈላሰፍ ያዙኝ ልቀቁኝ ብል፣ እንደወረደ እናገራለሁ ብዬ ባቅራራ አይሆንም፡፡ ምክንያቱም ስብሐት የተሠራበት ቀመር የሚያገለግለው፣ ለስብሐት ብቻ ነው፡፡ እኔ ደግሞ ሌላ ቀመር ነኝ፡፡ ብዙዎቹ በእሱ ፍቅር አበድን ብለው፣ የእሱ መንገድ የጥበብም የሕይወትም ነው ብለው ያመኑ፣ ከማመንም በላይ የተጠመቁ አጓጉል ሲወድቁ የምናየው ለዚህ ነው፡፡ የስብሐትን ጎዳና እንከተላለን ብለው ተነስተው ከጎዳናው አፈንግጠው እንደ ገል ተሰባብረው የወደቁ የትየለሌ ናቸው፡፡
ስብሐት፦ በኢትዮጵያ ምድር ሊደገም የማይችል፣ በእኛ እምነት ጥሩም መጥፎም ልማድና አስተሳሰብ የነበረው ደራሲ ነው፡፡ የስብሐት የቋንቋ አጠቃቀም ቀለል ያለ፣ እንደ ውኃ የሚጠጣ የማያነቅፍና ውብ ነው፡፡ ገፀ ባሕሪያቱን ሲያዋቅር ደምና ሕይወት በመስጠት ነው፡፡ የአእምሮው ምጡቅነት ገና፣ ገና አንብበንና ተመራምረን አንጨርሰውም፡፡ በኢትዮጵያ የድርሰት አፃፃፍ ያልተለመደ ጭብጥ፣ “እንዴ እንዲህም አለ እንዴ?” ሊያሰኝ የሚችል፣ ግርምትን የሚፈጥር የጥበብ መንገድ በማሳየት ስብሐት ፋና ወጊ ነው፡፡ ስብሐት ዝና ከአገር አገር የሚንቦገበገው፣ ኖቤል የሚያሸልመው ከዓመታት በኋላ ነው፡፡ ስብሐት የቀደደው የጥበብ መንገድ፣ ድንቅነቱ ፍንትው ብሎ የሚወጣው አዎ ወደፊት ነው፡፡ እነ አጋፋሪ እንደሻው፣ ኮምቡጡር…
ስብሐት መሞቱን የሰማሁ ዕለት አላለቀስኩም፡፡ ነገር ግን ማስቀበር እንዳለብኝ አምኜ ሎሚ ሜዳ ከሚባል ለኑሮዬም ለመቀበርያዬም ከመረጥኩት አካባቢ መጣሁ፡፡ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ከሰው በፊት ተገኝቼ፣ ከሰው በፊት ወጣሁ፡፡ “ለምን ወጣህ?” ካላችሁኝ መልስ አለኝ፡፡
በቅድስት ሥላሴ በወቅቱ በአፀደ ነፍስ በነበሩት አባታችን አቡነ ጳውሎስ አጋፋሪነት የተካሄደው የቤተ ክርስቲያንና የቀብር ሥነ ሥርዓት በፍፁም ሊዋጥልኝ አልቻለም፡፡ ምክንያቱም ስርዓቱ ረጅም ነበር።
በጥበብ ሐድራ ከገባ በኋላ ኃይማኖት ለስብሐት ምኑ ነበር? በእርግጥ በልጅነቱ በወላጆቹ ሣቢያ “ሥጋ ወደሙ” ተቀብሎ ይሆናል (ክርስትና መነሳቱን ሰምቻለሁ)፡፡
እኔ የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ አንዳንዴ የማምንበትን ሳይሆን፣ የሚያምኑበትን እከተላለሁ፡፡ የማልፈቅደው እንኳ ቢሆን ከማኅበረሰቡ የኑሮ ማዕቀፍ ላለመውጣት እተጋለሁ፡፡ በዚህም ባሕሪዬ በአደባባይ፣ “እኔ አድር ባይ ነኝ” ብዬ ተናዝዤ ንስሃ ከገባሁ ቆይቻለሁ፡፡ አድር ባይ ፀሐፊ እንደምን የጥበብ ማኅበርተኛ ሊሆን ይችላል? ካላችሁ፣ “የምወዳችሁና የማፈቅራችሁ ጥበበኞች ከልብ ካሰቡበት እምባ አይገድም፡፡ ይቻላል” እላችኋለሁ፡፡ ትንሽ ምሣሌ ልስጣችሁ፡፡ ወሲብን በሚመለከት የዕድሜ እርከን ተጠብቆ በግልጽ መነጋገር ቢቻል ደስ ይለኛል፡፡ በዚህም አቋሜ ከጓደኞቼ ከሠራዊት ፍቅሬ ጋር በገደብ፣ ከመሐልየ መሐልየ ዘ ካዛንቺስ ደራሲ ተድባበ ጥላሁን ግን ያለ ገደብ በነፃነት እናውራ፣ አንዳንዴም እንፈላሰፍ እንደነበር ትዝ ይለኛል፡፡ ተድባበ ነፍሱ ይማር ተአምረኛ ሰው ነበር፡፡ እኔና እርሱ ባለንበት “ታቡ” የሚባል የለም፡፡ ከሌሎች ወግ አጥባቂዎች ጋር ስደባለቅ ግን አመሌን በጉያዬ እይዛለሁ፡፡ እኔ በባህሪዬ በጣም ጥብቅ ዲሲፕሊን አላቸው ከሚባሉት ተርታ እንደምመደብ ይሰማኛል፡፡ “እኔ የማምነው በዚህ መንገድ ነው ብዬ ግን ከጀማው መነጠል አልፈልግም፡፡ አንድ ሰው ባጣሁ ቁጥር፣ አንድ ጣቴ የተቆረጠ ያህል ያመኛል፡፡ ለክርክር ስጋበዝ፣ አቋሜን ስጠየቅ ግን በይፋ ለማስረዳት እሞክራለሁ፡፡ በመሆኑም አድር ባይ ፀሃፊ ተገኘ ብላችሁ አደራችሁን “ጊነስ ቡክ” ላይ እንዳታስመዘግቡ፡፡ በጣም ብዙ ምክንያቶችና እውነቶች ስላሉኝ፣ ከፍርድ በፊት ቃሌን ብትቀበሉኝ ማለፊያ ነው፡፡ የለም እንፈርድብሃለን የምትሉም ከሆነ የጋዜጣ ገጽ ስለማይበቃ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር መድረኩን ያዘጋጅና ዲሞክራቲክ የሆነ ክርክር አካሂደን ሕዝበ ውሳኔ ይካሄድ፡፡
እኔ አልቃታለሁ እንጂ የስብሐት ገድል፣ የስብሐት ዘመን ተሻጋሪ ምልከታ አያልቅም፡፡ ስብሐት፣ ሞትን ሲሸሽ ኖሮ በሞት የተሸነፈ፣ ነገር ግን ድንቅ ሥራዎቹ ሞትን መቶና ሁለት መቶ ጊዜ ያሸነፈ ጊዜ የማይሽረው ደራሲ ነው፡፡ በእርግጥ በእኛ ዓይን የባህሪ ችግር ነበረበት ማለት እንችላለን፡፡ የማኅበረሰቡ እሴት፣ ወግና ልማድ መጠበቅ አልፈቀደም፡፡ ይሄ ደግሞ እምነቱም ፍላጎቱም አልነበረም፡፡ ስብሐት፣ በኢትዮጵያ ምድር ለጉድ ፈጥሮት ለጉድ አኖሮት ያመለጠን ደራሲ ነው፡፡ ስብሐት የሞተ ዕለት አላለቀስኩም ብያችኋለሁ፡፡ አሁን፣ አሁን ግን በዚች ምድር ቀድሞም፣ አሁንም ወደፊትም ወደር የማላገኝላት እናቴ ብዙነሽ ሐብቴንና ስብሐትን ባስታወስኩ ቁጥር አለቅሳለሁ፡፡ እንባዬ ጉንጬ ላይ ባይወርድም በሆዴ አነባለሁ፡፡ ወንድ ልጅ እፊቱ ላይ እንባ ከማውረድ ይልቅ ሆዱ ውስጥ ያለቅሳል?
በሃሳቡ በጣም የወደድኩት ሚካኤል፣ የስብሐት ነውር ብሎ ከገለፃቸው መካከል ብዙ ወጣቶች እሱን እንከተላለን ብለው ከመስመር መዛነፋቸው አንዱ ነው፡፡ እሱ ራሱም የስብሐት እንደነበር ጠቅሷል፡፡ ነገር ግን ማንነቱን ፈልጎ፣ የራሱን መንገድ አግኝቶ ከጀማው ተገነጠለ፡፡ የራሱን ዕድል በራስ የመወሰን መብት እስከ መገንጠል የተፈቀደ ነውና ይህ አቋሙን ልንኮንነው አይገባም፡፡ ነገርግን አቶ ሚካኤልን የምጠይቀው ስብሐት የሚናገረውን፣ የሚያወራውን፣ ውሎውን… ተመልክቶ ወዶና ፈቅዶ በገዛ ሥልጣኑ እጁን ሰጥቶ ተማርኮ ለደረሰበት ጉዳት ስብሐት ምን ያድርግ? ስብሐት፣ አይደለም ሌላውን የገዛ ራሱንም ጥሏል እያልነው ሌላውን የማዳን ሥራ እንደምን ሊሆንለት ይችላል? ስብሐት የቀይ መስቀል መልዕክተኛ እኮ አይደለም፡፡ ለተጎዱ ወገኖች ድንኳንና ቀለብ አያቀርብም፡፡ ስብሐት፣ ለየት ያለ የጥበብ ሰውና “ሕይወትን ከእነ ብጉንጇ” ማሳየት የሚችል ደራሲ ነው፡፡
እኔ ይህ ጽሑፍ የፃፍኩላችሁ ዳተኛ፣ ከስብሐት ጋር አንድም ቀን ቁጭ ብዬ በግንባር ተነጋግሬ አላውቅም፡፡ በ1986 ዓ.ም የዘንባባ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሳለሁ፣ “ልብ ያለው ልብ ይበል” የሚል ገጽ ላይ ስጽፍ አንድ ስታይል ለማውጣት ሞክሬ ነበር፡፡ “ይድረስ ለሰማይ ቤቱ አጋፋሪ እንደሻው፣ ግልባጭ ለምድሩ ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር -ደራሲ” በሚል ርዕስ ከሰማይ ቤት ወደ ምድር፣ ከምድር ደግሞ ወደ ሰማይ ቤት ጥበባዊ መልዕክት እንዲተላለፍ አደርግ ነበር፡፡ ገጹን የፈጠርኩት ለእርሱ በነበረኝ ፍቅርና ክብር ምክንያት ስለነበር፣ አንብቦት ከሆነ አስተያየት እንዲሰጠኝ ብዬ አንድ ቀን ስልክ ደወልኩለት፡፡ በትህትና ራሴን አስተዋውቄ፣ ርዕሰ ጉዳዩና ስታይሉን እንዴት እንዳገኘው ስጠይቀው ሰደበኝ፡፡ ለስድቡ ምላሽ በስክ ከመስጠት ተቆጥቤ በዚሁ ተለያየን፡፡ በዚህም ቂም ይዤበት በ17 ዓመታት የጋዜጠኝነት ዘመኔ አንድም ቀን ኢንተርቪው አድርጌው ወይም እርሱን የሚመለከት ጽሑፍ ጽፌ አላውቅም፡፡ በዚህ ሙያየዬ እጅግ ብዙ የጥበብ ሰዎችን ኢንተርቪው አድርጌያለሁ፡፡ ሚኒስትሮች፣ የመምሪያ ሥራ አስኪያጆች፣ ዘፋኞች፣ የተለያዩ ባለሙያዎች …፡፡
በወዳጄ ስንዱ አበበ አማካኝነት የስብሐት የታተሙና ያልታተሙ ሥራዎችን ቀደም ብዬ አንብቤ ልዩ ሥፍራና ክብር ሰጥቼዋለሁ፡፡ ታዲያ ስብሐትን ይህን ያህል አውቄው ኢንተርቪው አለማድረጌ ወይም በነበረኝ የመፅሔትና የጋዜጣ ምክትል ዋና አዘጋጅነት ስልጣኔ ኢንተርቪው እንዲደረግ አለማድረጌ ወይም ደግሞ ቀርቤ አለማነጋገሬ ጥፋት ነው ካላችሁም የምትቀጡኝን ቅጣት እስከ “ስቅላትም” ቢሆን፣ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለመቀበል ዝግጁነቴን ሳረጋግጥላችሁ ከልብ ነው፡፡ ቂመኛ የጥበብ ሰው ግን አለ? ሰላም ሁኑ!

Health: እህቴን ሔፕታይተስ ከውጭ ጉዞዋ ያስቀራት ይሆን?

$
0
0

እህቴን ወደ አሜሪካ ለማምጣት ያልቆፈርኩት ድንጋይ አልነበረም። ሆኖም አልተሳካልኝም። እርሷ በጣም ወደ ውጭ ለመሄድ ከፍተኛ ፍላጎት አላት። ካልሆነ ወደ አረብ ሃገርም ቢሆን ላከኝ በሚል ገንዘብ ልኬላት መሰናዳት ጀመረች። በኋላ ላይ ወደ ውጭ ለመሄድ ባደረኩት የጤና ምርመራ ሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› አለብሽ ተባልኩኝ አለችኝ። ወደ አረብ አገር ሄጄ ሰርታ ራሷን ለማሻሻል ባደረረባት ፍላጎት መሰረት በአንድ ኤጀንሲ በኩል እንቅስቃሴ ጀምራለች። ከጉዞዋ በፊት የተለያዩ የላብራቶሪ እና የአካል ምርመራዎች ኤች.አይ.ቪን ጨምሮ አድርጋ ሁሉን ነፃ ስሆን ሔፕታይተስ ‹‹ቢ›› የሚባል ሰምቼ የማላውቀው ችግር በደምሽ ይታያል ተባልኩ አለችኝ። ምን አይነት በሽታ ነው? ምንድነው የእህቴ የወደፊት እጣ ፈንታዋ?
የከበቡሽ ወንድም

የዶ/ር ዓብይ ምላሽ፡- ውድ ጠያቂያችን እህትህ በአጋጣሚ ለሜዲካል ቼክ አፕ ሄዳ የሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› (ሔፖታይተስ ‹‹B›› ሰርፌስ አንቲጅን) ከሌሎች ምርመራዎች መካከል ይህ ምርመራ በደምዋ ውስጥ የሔፖታይተስ ቫይረስ እንዳለ ጠቁሟል፡፡ በአጠቃላይ ወደ አምስት የሚደርሱ ሔፖታይተስ ‹‹A›› ሔፖታይተስ ‹‹B›› ሔፖታይተስ ‹‹C›› ሔፖታይተስ ‹‹D›› እና ሔፖታይተስ ‹‹G›› የተባሉ ጉበትን ለጉዳት የሚያጋልጡ የቫይረስ አይነቶች (cirrhosis) እስከ ጉበት ካንሰር በሄፖታይተስ B,C እና D የበሽታ ደረጃዎች ሊከሰቱ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ሁሉ የሔፓታይተስ ቫይረሶች የሚከፋፈሉት በሞለኪዩላቸው እና በአንቲ ጅን ፀባያቸው ነው፡፡
hepitates Bየ እህትህ ችግር የሚያያዘው ከሔፖታይተስ B ጋር ሲሆን ይህ ቫይረስ ከሌሎቹ አራቱ ይለያል፡፡ ይኸውም ሌሎቹ አር ኤን ኤ (RNA) ቫይረሶች ሲሆኑ ሔፖታይተስ ‹‹B›› ዲ.ኤን.ኤ ቫይረስ ነው፡፡ ሔፖታይተስ ‹‹B›› ከነሙሉ አካሉ ‹‹ዳን›› ፓርቲክል ሲባል 42 ናኖ ሜትር ይለካል፡፡ ይህም በኤሌክትሮን ማክሮስኮፕ እንደ ባክቴሪያዎች ለመታየት አያስችለውም፡፡ ቫይረሱም 22 ናኖ ሜትር የሚሆን የውስጥ አካል ሲኖረው ከላይ የሚሸፍነው ከፕሮቲን የተሰራ ሽፋን ወይም የሔፖታይተስ ቫይረስ ሽፋን አንቲጅን አለው፡፡
ይህም ሽፋን በቫይረሱ በተጠቁ የጉበታችን ሴሎች በብዛት ይመረትና በደማችንና በሰውነታችን ፈሳሾች ከቫይረሱ ተለይቶ መጠኑ 22 ናኖ ሜትር በሚሆን ብናኞች (particle) መልክ በብዛት ከቫይረሱ ውጭ ይሰራጫል፡፡ በጠያቂያችን ደም ውስጥ ሔፖታይተስ ‹‹B›› ቫይረስ እንዳለ የታወቀውም በዚህ የቫይረሱ ሽፋን አማካኝነት ነው፡፡
ሔፖታይተስ ‹‹B›› በቀጥታ የሰውነታችን ሴሎችን አያጠቃም፡፡ ነገር ግን በጉበታችን ላይ የሚደርሰው ጉዳት የሚፈጠረው የራሳችን መከላከያ ኃይል ቫይረሱን ለማጥፋት በሚከፍተው ጦርነት ነው፡፡
ሔፖታይተስ ‹‹B›› በመላው ዓለም ሲገኝ እስካሁን ከ2 ቢሊዮን በላይ ሰዎች ውስጥ እንዳለ ይገመታል፡፡ ይኸውም ከዓለማችን ከሶስት ሰዎች መካከል በአንዱ ውስጥ አለ እንደ ማለት ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ ወደ 300 ሚሊዮን የበሽታው ተሸካሚ እንዳሉ ይገመታል፡፡ አሜሪካ እና እንግሊዝ ዝቅተኛ የተሸካሚ ቁትር ሲኖራቸው ማለትም ከአንድ ሺ ሰዎች መካከል አምስቱ የተያዙ ሲሆን በአፍሪካ በመካከለኛውና በሩቅ ምስራቅ ኤሺያ የተሸካሚ ቁጥር 15 በመቶ ይደርሳል፡፡
ይሄ ቫይረስ የሚተላለፈው በደም (ማለትም ለበሽተኛ የተበከለ ደም ሲሰጥ፣ የተበከለ መርፌ በመጠቀም፣ በተበከለ ስለት ንቅሳት ሲደረግ)፣ ከታማሚው ጋር የቅርብ ግንኙነት (ንክኪ)፣ የግብረ ስጋ ግንኙነት (በተለይ የግብረ ሰዶም) ናቸው፡፡ ስለዚህ መተላለፊያው መንገድ ከኤች.አይ.ቪ ጋር ሲመሳሰል የጤና ባለሙያዎች በስራ ጊዜ ከበሽተኛ ፈሳሽ ጋር በሚያደርጉት ግንኙነት በኤች.አይ.ቪ የመያዛቸው ዕድል ወደ 2 በመቶ ሲሆን ሔፖታይተስ ‹‹B›› ግን 35 በመቶ ነው፡፡ በተጨማሪም በወሊድ ጊዜ ከእናት ወደ ልጅ ይተላለፋል፡፡
በአብዛኛው በዚህ ቫይረስ የተለከፈ ሰው በሽታው አይታይበትም፡፡ ቫይረሱ (ሔፖታይተስ ‹‹B›› በደሙ/ዋ ውስጥ መኖሩ የሚታወቀው በአጋጣሚ በሚደረግ የጤና ቼክአፕ ምርመራ ነው፡፡ በጠያቂያችን እህትም የተፈጠረው ይኸው ነው፡፡ ነገር ግን አንዳንዴ ቫይረሱ በርካታ የህመም ስሜት ይፈጥርና ተጠቂው ወደ ሐኪም ዘንድ ይመጣል፡፡ በመጀመሪያም በሽተኛው የህመም ስሜት ይሰማዋል፣ ቋቅ ቋቅ ይለዋል፣ ምግብ ያስጠላዋል፣ ሲጋራ የሚያጤስ ከሆነ ሲጋራ ያስጠላዋል በዚህ ጊዜም አይኑ ላይ ቢጫ የመሆን ምልክት አያሳይም፡፡ ከአንድ ወይም ከሁለት ሳምንት በኋላ አንዳንድ በተለምዶ የወፍ በሽታ የሚባለው ሌላው የህመም ስሜታቸው ጎልቶ ይታያል፡፡
የዓይን ቢጫ መሆኑ እየደመቀ ሄዶ ሽንት ጠቆር ሰገራም ነጣ ይላሉ፡፡ ጉበትና ቆሽት መጠነኛ ማበጥ ያሳያሉ፡፡ አልፎ አልፎ የንፍፊቶች ማበጥ ሊታይ ይችላል፡፡ ከዚህ በኋላ የዓይን ቢጫ መሆን በራሱ ጊዜ እየጠፋ ታማሚው ከሶስት እስከ ስድስት ሳምንታት ይሻላታል ወይም ይሻለዋል፡፡ ከጉበት ውጭ በጣም አልፎ አልፎ፣ መገጣጠሚያ፣ የደም ስሮች፣ የልብ ግድግዳ፣ ኩላሊትንም ሊጎዱ ይችላሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ በሽታው ሊያገረሽ ሲችል በዚህን ጊዜ የዓይን ቢጫ መሆኑ በድጋሚ ይከሰታል፡፡ በጣም አልፎ አልፎ በሽታው ጉበትን እጅግ አጥቅቶ አጣዳፊ ደረጃ ደርሶ የጉበት ኮማ የሚባል ፈጥሮ በሽተኛውን ሊገድለው ይችላል፡፡
10 በመቶ የሚሆኑት አክዩት ሔፖታይተስ ‹‹B›› (acute hepatitic B…) በሽታ የያዛቸው ደግሞ በሽታው ወደ ክሮኒክነት (Chronic Hepatitic B infection) ይለወጥባቸዋል፡፡ ከዚህም ውስጥ ከ70-90 በመቶ የሚሆኑት ጤናማ ተሸካሚ ሲሆኑ ጠያቂያችን ከዚህ ግሩፕ እንደምትመደብ እገምታለሁ፡፡ ሌሎቹም ክሮኒክ ከሆነባቸው ከ10-30 በመቶ የሚሆኑት ክሮኒክ ሔፖታይተስ የሚባል ደረጃ ሲደርሱ ከዚያም የጉበት መሸብሸብ (Cirrhosis) ብሎም የጉበት ካንሰር (Hepatocellular carcinoma) ይሆንባቸዋል፡፡ ነገር ግን ጤነኛ ተሸካሚ ይሆናሉ ከተባሉ ስንቱ ወደ ፊት የጉበት ካንሰር ከጊዜ ብዛት እንደሚይዛቸው ገና ግልፅ አይደለም፡፡
ድንገተኛ የሔፖታይተስ ‹‹B›› ኢንፌክሽን (የወፍ በሽታ) የሚታይበት ታማሚ ወደ ሐኪም ዘንድ ሲሄድ የተለያዩ ከጉበት ጋር የተገናኙ የደም ምርመራዎ፣ ሌሎች የአንቲቦዲ ምርመራዎች፣ የሽንት ምርመራ ወዘተ… ይደረግለታል፡፡ ሌሎች ተቀራራቢ ምልክት የሚያሳዩ በሽታዎች መኖር አለመኖራቸው መረጋገጥ አለባቸው፡፡
ወደ ክሮኒክነት ያልተለወጠ አክዩት ሔፖታይተስ ከድጋፍ ሰጪ ህክምና በስተቀር አያስፈልገውም፡፡ ከላይ እንደተጠቀሰው በራሱ ጊዜ እየዳነ ይሄዳል፡፡
ክሮኒክ የሆነ ሔፖታይተስ ‹‹B›› ኢንፌክሽን ያላቸው ታማሚዎች መታከም አለባቸው፡፡ የህክምናውም አላማ ሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› እና ‹‹ኢ›› የተባለውን አንቲጂን እና የሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› ቫይረስ ዲኤንኤ ከደም ውስጥ ማጥፋት ነው፡፡ ይህም በጉበት ሴሎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ይቀንሰዋል፡፡ ሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› ቫይረስ ዲ.ኤን.ኤ ከደም ውስጥ ማጥፋት ነው፡፡ ይህም በጉበት ሴሎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ይቀንሰዋል፡፡ ሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› እና ‹‹ኢ›› አንቲጅን ከደም ውስጥ ከጠፋ የበሽታው የመመለስ ዕድል ይቀንሳል፡፡ ታማሚው ከደሙ ሔፖታይተስ ‹‹ቢ›› እና ‹‹ኤስ›› አንቲጅን ቢታከመውም በደም ውስጥ ቆይቶ የበሽታው ተሸካሚ መሆኑ ይቀጥላል፡፡ አብዮተኞቹ ግን በስተመጨረሻም ይሄም አንቲጅን ከደማቸው ይጠቀፋላቸዋል፡፡
አሁን አሁን በየዓመቱ አዳዲስ መድሃኒቶች ይህንን ክሮኒክ ሔፖታይተስ ለማከም ፈቃድ እየተሰጣቸው ሲሆኑ ዋና ዋናዎቹ መድሃኒቶች አልፋ ኢንተርፌሮን (a interferon) እና ፀረ ቫይረስ (anti viruses) ናቸው፡፡
መከላከያው ለበሽታ የማያጋልጡ ሁኔታዎችን ለምሳሌ የተበከሉ (ሊበከሉ የሚችሉ መርፌዎችን) ማስወገድ፣ በርካታ የግብረ ስጋ ጓደኞችን መተው (ልቅ የግብረ ስጋ ግንኙነት ማስወገድ)፣ ለበሽተኛ የሚሰጥ ደም ከቫይረሱ ነፃ መሆኑን ማረጋገጥ፣ የጤና ባለሙያዎች ከበሽተኛ የአካል ፈሳሽ ጋር ያላቸውን ግንኙነት መቀነስ ወይም ጓንት መጠቀም እና ክትባት መውሰድ ናቸው፡፡

የማለዳ ወግ …ይነጋል ጨለማው … !

$
0
0

የመውጫ ቪዛ_02(2)-1-1-1
ከነብዩ ሲራክ

የጨለመ ቀን ይነጋል ፣ ክፉ ቀን ያልፋል ! የሃገር መሪዎች ለህዝብ ቆመው ትክክለኛ ምርጫ እንኳ አድርገው ስልጣናቸውን ለተተኪው ትውልድ ባያስተላልፉ ሲያረጁና ሲያፈጁ ጥቅማቸውን የሚያስከብርላቸው ተክተውም ቢሆን መሸኘታቸው አይቀሬ ነው! ለህዝብ እና ለሃገር ብሔራዊ ጥቅም ያለተጋ መንግስት በተቀያየረ ቁጥር በዜጎች ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ይህ ነው የማይባል ተጽዕኖን ያሳድራል። ተጽኖ አድራጊነቱ የሚከወነው በዋናነት በመንግስት መሆኑ ባይካድም ለሆዳቸው ያደሩ አጎብጓቢ የአበራካችን ክፋዮች የነዋሪው ውሎ አዳር ላይ የሚያደርሱት ተጽዕኖ እንዲህ በቀላሉ ሊገልጹት የሚችሉት አይደለም! አይቻልምም ! በዘመነ ደርግ ከስርአቱ በላይ አድርባዮች ለስርአቱ ያላቸውን ታማኝነት ለማሳየት ሲሉ ብቻ በገዛ ወገናቸው ላይ ይፈጽሙትን የነበረው ግፍ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው!
ያ ዘመን አከተመ ብለን ትንሽ ሳንተነፍስ ዛሬም በሌላ አደጋ ተዘፍቀናል ። ወደ ትላልቁ ጉዳይ አልገባም ። ዛሬ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ዜጎች በዘመናዊ ባርነት ከህግ ማዕቀፍ ውጭ ስለመሸጣቸው እማኝ በሆንኩበት የአረብ ሃገር ኑሮ የራሳችን ዜጎች መብት ይከብር ብሎ መብታችን ለማስከበር ሃላፊነታቸውን ስላማይዋጡ ሃላፊዎች መናገር ሃጢያት ሆኖ ያስወነጅላል ! ” ህገ መንግስት አልተከበረልንም!” ያሉ ሰላማዊ ዜጎች በተሰጣቸው የህግ ማዕቀፍ መሰረት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግን ተከልክልው እየተመለከትን ነው ። እኔ እሰከማውቀው እና በአደባባይ ሲነገር እንደሰማሁት አንድ መንግስት በስደት ላይ ያሉ ዜጎቹ ስቃይ ይሰማዋል። ግን ስቃዩን ለማስቆም የሚችሉ ተወካዮችን በአረብ ሃገር ከማሰማራት ጀምሮ በሃገር ቤት የሚሰራውን ለእድሜ ያልደረሱ ታዳጊ እህቶቻችን በደላሎች ወደ አረብ ሃገራት እየተጋዙ የሚፈጸመውን ግፍ ተከታትሎ ማስቆም አልቻለም ። መንግስት ያላቻ ጋብቻ አይፈቀድም እያለ በቤተሰብ አማካኝነት የሚመሰረት ትዳርን ህገ ወጥ ነው ብሎ ማገዱ ባይከፋም ትዳር እንዳትመሰርት በእድሜዋ ምክንያት የተከለከለችው ጉብል ወደ አረብ ሃገር ለስራ ብቁ የሚያደርግ እድሜ ቆልላ እዚህ ሳውዲ አግኝቻት አጫውታኛለች ። ብዙዎች አንድ አይነት ባይሆን በለያዩ መንገዶች በሚከወን ሂደት ይሰደዳሉ ። የድልላ ስራው ከሃገር ቤት እሰክ ውጭ ሃገር በስርአቱ ደጋፊዎች የሚመራ በመሆኑ እንቅስቃሴው በግፍ ሲካሔድ ይህም የስደቱን ኑሯችን እየከፋ ለመሔዱ እማኝ ከሆነን መልካም ነው ።
መንግስት በራሱ ሰአት ከፖለቲካ ፍጆታ ላላለፈው ጥቅም የሚያሳየን የከፋ የስደት ኑሮ ይቀየር ዘንድ የሚሰራው ስራ አያበረታታም። የመንግስት ተወካተዮቻች እንኳንስ ችግር ብሶታችን ሰምተው ሊያሰሙ ፣ እንዳንሰማ እንዳናይ እንዳንሰማ ማግለል ይዘዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከፍተኛ ሃላፊዎች በተደፈጋጋሚ ወደ ሳውዲ ቢመጡም ነዋሪውን አያጋኟቸው ። መረጃ ሰበሰብን ብለው የሚሔዱት ፍትሃዊ የመብት ጥበቃ ከማያደርጉት ሃላፊዎች፣ ከፖለቲካ ካደሬዎችና በልማት ስም ከተደራጁ ማህበራት በመሆኑ ለቀጠለው ችግር መፍትሔ ሊያገኙለት አልቻሉም ! ግፍ ቢበዛም አቤት የሚባልበት ቦታ አጥተናል !የሚነገር የሚጻፈውን አልሰማ ላለ መንግስት ደግሞ የዜጎችን መብት ስል ማስከበር ህገ መንግስቱ የሰጠውን መብት መጠቀምና ጥያቄን ማቅረብ ተገቢ ነው። ተቃውሞን በሰላማዊ ሰልፍ ማቀርብ ደግሞ ብቸኛው ተገቢ መንገድ ነው። ይህንም መብት በመንግስት ስለመራቁና እዚያ ለመድረስ መሔድ ያለብንን ጉዞ አርቆ አጥቦታል! ህዝብ መብቱን ለመጠቀም መንገዱ ከጠበበበት ደግሞ አመጻና የከረረ ተቃውሞን በማምጣት ሃገርን ወደ ሁከት ህዝብን ወዳለመረጋጋት ይገፋልና ተገቢ አይደለም ! በጃንሆይ የሆነው በደርግ ፣ በደርግ የነበረው ተጠናክሮና መንገዱን ቀይሮ በኢህአዴግ መንግስት እየተሰራበት ያለው የመብት ገፈፋ ቆሞ ላስተዋለው ያማል! ሰው በነፃ ሃሳቡ ፣ለሃገሩ ይበጃል ያለውን በግልና በቡድን ህጋዊ በሆነ መንገድ ተደራጅቶ ድምጹን ሰላሰማ ዛሬም ይታሰራል ፣ይደበደባል ፣ ይገደላልም ! ይህ ሁሉ አውጥቸ አወረድኩና ቢከፋኝ በማለዳ ወጋወጌ የዘመን ሂደት ፣ የሰው ለሰው ጉድኝት ትዝብቴን ለማዘከር ” የጨለማው ይገፋል ይነጋል ” ስል ስንኝ ቢጤ ቋጥርኩ …. ይህም ይገኝበታል …
ይነጋል …
“ይሁን ያልፋል ! ” ብለን ዝም ብለን በቻልነው
ያንዱ ቤት ሲፈርስ ባያመው ያ ሌላው
የወገኑ እንግልት ዘልቆ ባይሰማው
ግፍና በደሉ እሱን ሰላልነካው
ነግ በኔን ዘንግቶ አይኑን ቢሸፍነው
ጀሮው እየሰማ “አልሰማሁም “ቢለው
አይን አይቶ እንዳላየ ለእይታ ቢያገለው
የዘመን ክፉ አለው ፣ የዘመን ደግ አለው
እንደከፋ አይቀርም፣ ይነጋል ጨለማው !
ከህሊና ፍርጃ ማያስሸሽ መከራው!
ብርሃን ይመጣል ይነጋል ጨለማው!
(ሙሉውን ግጥም ከዚህ ጋር ተያይዟልና ያንብቡት! )
ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live