Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

በአዲስ አበባ ሕዝብን ሲቀሰቅሱ የነበሩ 5 ሰዎች ታሰሩ

$
0
0

“እኔ በአዋጅ ሳይሆን በትዕዛዝ ነው የምመራው፤ እሰር የሚል ትዕዛ ደርሶኝ አስሬያቸዋለሁ”

- የፖሊስ አዛዥ

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

(ዘ-ሐበሻ) የፊታችን እሁድ ነሐሴ 19 ቀን 2005 ዓ.ም (ኦገስት 25 ቀን 2013) በአዲስ አበባ በሚገኘው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት/መ.ኢ.አ.ድ/ ዋና ጽ/ቤት 33ቱ ፓርቲዎች ለጠሩት ህዝባዊ ውይይት የመኪና ላይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ የፓርቲዎቹ አባላት በህገወጥ መንገድ መታሰራቸውን የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት አስታወቀ።

እንደ ዘገባው ከሆነ በቅስቀሳው ላይ ከነበሩት ወገኖች መካከል
1ኛ አቶ ደመላሽ፣
2ኛ. አቶ አብርሃም ፣
3ኛ. አቶ አታላይ በለው፣
4ኛ. አቶ እዮብዘር
5ኛ. አቶ መላኩ መሰለ
የተባሉት አባላት የቅስቀሳ መከናውን ከያዘው ሹፌርና ረዳት ጋር ታስረዋል፡፡
የፓርቲዎቹ አመራሮች አባሎቻቸው ወደታሰሩበት 1ኛ ፖሊስ ጣቢያ አቅንተው እስሩ ህጋዊ አለመሆኑን አዋጅ በመጥቀስ ቢያስረዱም በስፍራው የነበሩት የፖሊስ አዘዥም “እኔ በአዋጅ ሳይሆን በትዕዛዝ ነው የምመራው፤ እሰር የሚል ትዕዛ ደርሶኝ አስሬያቸዋለሁ” የሚል ምላሽ እንደሰጣቸው የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘገቧልል።


Sport: ሙስሊም ተጨዋችና እግርኳስ

$
0
0

ከሊሊ ሞገስ 

(በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 54 ላይ ታትሞ የወጣ)

ፓፒስ ዴምባ ሲሴ ሃይማኖቱን አSulley Muntari 22866 36713 427008_297185783682762_1437296408_n Egyptian-soccer-player images papis sise muslimጥባቂ ሙስሊም ነው፡፡ እስልምና ደግሞ ወለድን መብላት ይከለክላል፡፡ የወለድ ስርዓት ያለበት የፋይናንስ አሰራር ውስጥ ተከታዮቹ እጃቸውን እንዳያስገቡ ይደነግጋል፡፡ ኒውካስል ዩናይትድ wonga ከተባለው ኩባንያ ጋር የማሊያ ላይ ስፖንሰርሺፕ ስምምነት መፈራረሙ ለሲሴ አመቺ አልሆነም፡፡ ኩባንያው የአጭር ጊዜ ብድር የሚሰጥና ከፍተኛ ወለድን የሚጠይቅ ኩባንያ ነው፡፡ ኒውካስል ደግሞ የሲሴ ቀጣሪና ደመወዝም ይከፍለዋል፡፡ የሲሴ እምነት ደግሞ ከwonga ጋር ምንም አይነት የስራ ግንኙነት መፍጠርን አይፈቅድም፡፡ በዚህ ላይ በጨዋታዎች ላይ የኩባንያው አርማ የሰፈረበትን ማሊያ ለብሶ የመጫወት ግዴታ አለበት፡፡

የተጨዋቹ ተቃውሞ ከመነሻው ጠንካራ ነበር፡፡ ማሊያውን አልለብስም በሚለው አቋሙ መጽናቱን ለማሳየት ክለቡ ለቅድመ ውድድር ዘመን ዝግጅት ወደ ፖርቹጋል ያደረገው ጉዞ አካል አልሆነም፡፡ ጓደኞቹ ወደ ዝግጅት ሲጓዙ ሲሴ ቀርቶ ከቤተሰቦቹ፣ ከጓደኞቹና ከሃይማኖት ሊቃውንት ጋር በጉዳዩ ዙሪያ መከረ፡፡

በዚህ መልኩ ተቃውሞን ሲያቀርብ ሲሴ የመጀመሪያው እግርኳስ ተጨዋች አይደለም፡፡ በ2006 ለስፔኑ ሲቪያ በሚጫወትበት ጊዜ ፍሬዲሪክ ካኑቴ 888.com የሚል ፅሑፍ የሰፈረበትን ማሊያ እንደማይለብስ አስታውቋል፡፡ የኢንተርኔት ቁማር ኩባንያ በመሆኑ ነው፡፡ እንደ ሲሴ ሁሉ የእስልምና እምነት ተከታይ የሆነው ካኑቴ ደግሞ ይህን በማድረግ የመጀመሪው ስፖርተኛ አልነበረም፡፡ ሃሺም አምላ የተሰኘው ደቡብ አፍሪካዊ የክሪኬት ተጨዋች castle lager የተሰኘውን ቢራ ጠማቂ የኩባንያ ዓርማ የሰፈረበትን መለያ ከመልበስ ታቅቧል፡፡

እስልምና በምንም አይነት መጠን ቢሆን አልኮልን መጠጣትንም ሆነ ለሌሎች እንዲጠጡ ማበረታትን ይከለክላል፡፡ እናም አምላ ከማሊያው ላይ ምልክቱ እንዲነሳለት ጠይቋል፡፡ አስተዳዳሪውም የስፖርተኛውን ጥያቄ ተቀብለው በጨዋታ ላይ አምላ ማስታወቂያ ያላፈረበትን ማሊያ ለብሶ ተጫውቷል፡፡

የሲሴ ጥያቄ የአምላ አይነት ተቀባይነት አላገኘም፡፡ ዘግይቶም ማሊያውን ለመልበስ ወስኗል፡፡ ይሁን እንጂ ሲሴ አቋሙን የቀየረበት ምክንያት ዝርዝር አልታወቀም፡፡ ይልቅ ከፖርቹጋል ዝግጅት በቀረበት ሰዓት የብሪታኒያ ጋዜጦች ተጨዋቹ በካዚኖ (የቁማር ማዕከል) ሳለ የሚያሳይ ፎቶግራፍ በአምዶቻቸው ላይ አትመው ነበር፡፡ ፎቶው ሴኔጋላዊው ቁማሩን ሲጫወት ባያሳዩም ከመቆመሪያው ጠረጴዛ አጠገብ (በሚጫወት ሰው ሁኔታ) ተቀምጦ ነበር፡፡ ቁማሩን ተጫውቶ ከሆነ ማሊያውን ላለማድረግ የነበረው አቋም ከልብ አይደለም የሚሉ አስተያየቶች ተሰንዝረውበታል፡፡ ሆኖም የተጫዋቹ ወኪል ‹‹ሲሴ ቁማርተኛ አይደለም›› ሲል ማስተባበያ ሰጥቶለታል፡፡ የካዚኖው ኩባንያ ቃል አቀባይ ግን ሲሴ ከአንድ ጊዜ በላይ ወደ ቁማር ቤት ለመምጣቱ ማረጋገጫ ሰጥቷል፡፡ በቁማር ቤት መገኘቱን እንጂ ቁማር መጫወቱን ግን አልገለፀም፡፡

የኒውካስል ከተማ ከንቲባ ዲፑ አሃድ ሲሴ ማሊያውን አልለብስም ባለበት ሰዓት ላይ ለተጨዋቹ ድጋፋቸውን ሰጥተው ነበር፡፡ በኋላ አቋሙን መቀየሩ ግን ሰውየውን ለትችት የዳረጋቸው ይመስላል፡፡ በተለይ በቁማሩ ቤት የመገኘቱ ዜና ከንቲባውን አበሳጭቷቸዋል፡፡ አሃድ ለቢቢሲ በሰጡት መግለጫ እንዲህ ብለዋል፡፡ ‹‹በድርጊቱ በጣም አፍሬያለሁ፡፡ እኔ ብቻ ሳልሆን በአቋሙ የደገፉትን ሁሉ አሳፍሯል፡፡ በቁማር ቤት መገኘቱ (ቁማር ባይጫወትም እንኳን) መጥፎ መልዕክት ያስተላለፈ ይመስለኛል››

ለሃይማቱ ተከታዮች ፆም ሌላው ግዴታ ነው፡፡ ከፀሐይ መውጫ እስከ መጥለቂያ ድረስ ከምግብ፣ መጠጥ፣ ማጤስ እና ወሲብ መፈፀም መራቅ ግድ ነው፡፡ በረመዳን ወር ሙስሊሞች በዚህ ይተጋሉ፡፡ ወቅቱ የፀሎት ጊዜም ነው፡፡ በዚህ ወር ሙስሊሞች ከበዛ መዝናናት ሳይቀር ይታቀባሉ፡፡

ለስፖርተኞች ደግሞ ፈታኝ ጊዜ ነው፡፡ አንዳንዶች ጭራሹኑ አይጾሙም፡፡ ሌሎቹ ደግሞ የመጣውን ሁሉ ተጋፍጠው ይፆማሉ፡፡

ከማይፆሙት መካከል አንዱ ኒኮላ አኔልካ ነው፡፡ በፆም ወቅት ጉዳት እንደሚደራረብብኝ አረጋግጫለሁ ያለው ፈረንሳዊ የማይፆምበትን ምክንያት አቅርቧል፡፡ አንዳንድ አሰልጣኞች ደግሞ ተጨዋቾቻቸው እንዳይፆሙ ይከለክሏቸዋል፡፡ እንደማሩዋን ሻማክ ያሉት ደግሞ የአሰልጣኞችን ትዕዛዝ ወደ ጎን በማለት የሃይማኖታቸውን ግዴታ ይወጣሉ፡፡ በአንድ ወቅት ካኑቴ ሲናገር ‹‹በፆሙ ወቅት የማደርገውን ሁሉ የቡድን ጓደኞቼ በአንክሮ ይከታተላሉ›› ብሏል፡፡ ይከታተሉ እንጂ በፀሎቱ ጊዜ አይረብሹትም፡፡ እምነቱን ያከብሩለታል፡፡ ‹‹ስለዚህ እየጾምኩኝ መጫወቴ የተለመደ ነው›› ይላል፡፡

ሙስሊም ተጨዋቾች በረመዳን ወር በተቻላቸው መጠን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ቢገደቡላቸው አይጠሉም፡፡ ፆሙን በአግባቡ ለመፆም ሲሉ ነው፡፡ በአብዛኛው በሙስሊሞች የተገነባ ቡድን ያለው የግብፁ አል አህሊ ክለብ ጥሩ ምሳሌ ነው፡፡ የካይሮው ክለብ በአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ ከኦርላንዶ ፓይሬትስ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ከሐምሌ 28 ወደ ነሐሴ 3 ቀን 2005 እንዲቀየርለት ጠይቆ የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን ጥያቄውን ተቀብሎ ቢሆን ኖሮ ጨዋታውን ከፆሙ መጠናቀቅ በኋላ ይደረግ ነበር፡፡ ሆኖም ካፍ ጨዋታው በተያዘለት መርሐ ግብር እንዲቀትል (እንዳይቀየር) ወስኗል፡፡

አፍሪካዊያን እግርኳስ ተጨዋቾች ሁሉ ሙስሊሞች አይደሉም፡፡ ወይም ሙስሊም ተጨዋቾች ሁሉ አፍሪካዊያን ናቸው ማለት አይደለም፡፡ ግን የአፍሪካዊያን ሙስሊም እግርኳስ ተጨዋቾች ቁጥር ብዙ ነው፡፡

muslimpopulation.com እንደተሰኘው ድረገፅ መረጃ ከሆነ ከግማሽ በላይ አፍሪካዊያን የእስልምና እምነት ይከተላሉ፡፡ ለእንግሊዝ አገር ሙስሊም ተጨዋቾች ሃይማኖታዊ ግዴታቸውን በመወጣት እንዲጫወቱ ለማድረግ ድጋፍ ሰጪ ተቋም አላቸው፡፡ ቀድሞ ያልነበረውን ይህን አገልግሎት የሚሰጠው ተቋም በ2011 ናታን ኤሊንግተን በተባለ የክሪው አሌክሳንድራ አጥቂ የተመሰረተው የሙስሊም ተቋም በ2011 ናታን ኤሊንግተን በተባለ የክሪው አሌክሳንድራ አጥቂ የተመሰረተው የሙስሊም እግርኳስ ተጨዋቾች ማህበር ነው፡፡ በሊቨርፑሉ የስፖርት ህክምና ቡድን ኃላፊ ተጨዋቾች ምን ማድረግ እንዳለባቸው ምክር ይሰጣል፡፡ በማፍጠሪያ ሰዓት ጥቂት ብቻ እንዲመገቡና በኋላም በዛ ያለውን ምግብ እንዲያስከትሉ የዶክተሩ መመሪያ ይመክራል፡፡ በተጨማሪም ማህበሩ ከቢቢሲ ጋር በመተባበር ‹‹THE MUSLIM PREMIER LEAGUE›› የተሰኘ ጥናታዊ ፊልም ለማዘጋጀት እየሰራ ይገኛል፡፡ ፊልሙ በእንግሊዝ ከፍተኛው የእግርኳስ ዲቪዚዮን ውስጥ ሙስሊም ተጨዋቾች የሚገጥማቸውን ጉዳዮች ይዳስሳል፡፡ በ20 ዓመቱ የሊግ ታሪክ ሊጉ በሙስሊም ተጨዋቾች ላይ ያሳደረውን አዎንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖ ሁሉ በፊልሙ ላይ ይዳስሳል፡፡

ኢሕአዴግ እሁድ በአ.አ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ፤ ድምጻችን ይሰማ “መንግስት ሙስሊሙን እየዘለፈ ነው”አለ

$
0
0

hailemariam and samora(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ዛሬ እንደዘገበው “አክራሪዎች በእምነት ስም የህዝብን ሰላም ለማደፍረስ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በመቃወም እሁድ ነሃሴ 27/2005 ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግ የአዲስ አበባ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ገለፀ” ብሏል። በሌላ በኩል ድምጻችን ይሰማ “አክራሪነትን ለመዋጋት ተብለው በተዘጋጁ ስብሰባዎች ጸረ እስልምና የሆኑ ዘለፋዎች እተበራከቱ ነው!” ሲል ተቃውሞውን አሰማ።

ኢሕአዴግ የፊታችን እሁድ በአዲስ አበባ የጠራው ሰልፍ ሁሉም የሀይማኖት ተከታዮች በሰላም አብሮ ለመኖር ያላቸውን ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ሲል ድምጻችን ይሰማ በበኩሉ “ለእስልምና ጥላቻ ያላቸው የመንግስት ሃላፊዎችና ካድሬዎች አጋጣሚውን የእስልምናን ሃይማኖት ለማራከስ ተግባር እያዋሉት ነው” ብሎታል።

“ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ በእምነት ስም የሀገሪቱን ሰላም ለማደፍረስ ጥረት የሚያደርጉ አካላትን በመቃወም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በተደጋጋሚ ሰላማዊ ሰልፍ መደረጉ የሚታወስ ነው፡፡” ሲል የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ሲዘግብ ድምጻችን ይሰማ በበኩሉ “መንግስት አክራሪነትን ለመዋጋት በሚል እያዘጋጃቸው ባሉ ስብሰባዎች የእስልምና ሃይማኖት ላይ ዘለፋዎች እየተሰነዘሩ ነው፡፡ በየክፍለ ከተማውና ወረዳዎች ለካድሬዎች እና የሀይማኖት አባቶች ተብለው በሚካሄዱ ስብሰባዎች ‹‹የእስልምና ሃይማኖት የአክራሪዎች መፈልፈያ ነው››፣ ‹‹እስልምና የሚባል ነገር ነው ሰላም የነሳን›› ከሚሉ ተነስቶ ሌሎችም በርካታ ስድቦች እና ዘለፋዎች እየተንጸባረቁ ነው፡፡ በተለይ ባለፈው ረቡእና ሐሙስ የአዲስ አበባ ፍትህና ጸጥታ ቢሮ ባዘጋጀውና በስድስት ኪሎ ስብሰባ ማእከል በተደረገው ስብሰባ ሲንጸባርቅ የነበረው ስሜት ሕዝቡ ያወረዳቸው የመጅሊስ ሹመኞችን ጨምሮ ኢማሞችን ሁሉ አንገት ያስደፋ እንደነበር ታውቋል፡፡ ብዙዎችንም የመንግስትን አካሄድ በድጋሚ እንዲያጤኑት የጋበዘ ሆኗል፡፡” ብሏል።
muslim1

“የሁሉም ሀይማኖት ተከታዩች በተገኙበት የሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ የሀይማኖት ተከታዮቹ አብሮ በሰላም ለመኖር ያላቸውን ቁርጠኝነት ማሳያ መሆኑን የአዲስ አበባ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጽ/ቤት ቦርድ ሰብሳቢ ርዕሰ ደብር በርሁን አርአያ ገልጸዋል” ሲል ዜናውን ያተተው ኢቲቪ የሀይማኖት እኩልነት ባልተከበረበት ወቅት ጭምር ህዝቡ ጠብቆ ያቆየውን የመቻቻልና የአብሮነት እሴት ጥቂት አክራሪዎች ለማደፍረስ መሯሯጣቸውን ለመቃወም ሁሉም የሀይማኖት ተከታዮች በዕለቱ እንደሚሳተፉ ርዕሰ ደብር በርሁን አርአያ ጠቁመዋል ካለ በኋላ እሁድ 27/2005 በሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ የሁሉም ቤተ እምነት መሪዎች እና ተከታዮቻቸው የሰላም መልእክቶችን በመያዝ ከየአቅጣጫው ወደ መስቀል አደባባይ ያመራሉ ተብሎ ይጠበቃል” ሲል ዘገባውን አጠናቋል።

ድምጻችን ይሰማ በበኩሉ “በዚህ በቢሮ ሀላፊው አቶ ጸጋዬ ሀይለማርያምና በደህነነት መስሪያ ቤት ሀላፊዎች በተመራው ስብሰባ የተገኙና ቀድመው ንግግር የሚያደርጉበት አጀንዳ የተሰጣቸው የፓርቲ ካድሬዎች በከፍተኛ ሁኔታ የእስልምናን ሃይማኖት የሚያራክሱ ንግግሮች ሲያደርጉ ከመታየታቸውም በላይ አንዳንዶች ለእስልምና ያላቸውን ጥላቻ ከመግለጽ ጭምር አንኳ አልተቆጠቡም፡፡ የሱና ምልክት የሚንጸባረቅባቸው አካላትን መንግስት ሊታገላቸው እንደሚገባ ያሳሰቡት እነዚህ ካድሬዎች የእስልምና ሃይማኖት መንፈሳዊ ተግባራትን ሁሉ የአክራሪነትና አሸባሪነት መገለጫዎች አድርገው ሲፈርጇቸው ተደምጧል፡፡ አቶ ጸጋዬ ኃይለማርያም ከመንግስታዊው ሃይማኖት የማጥመቅ ዘመቻ ጀምሮ ሙስሊሙን ህብረተሰብ ሲዘልፉና በሙስሊሞች መካከል የልዩነት እሾህ ለመትከል ሲሯሯጡ የቆዩ ግለሰብ እንደሆኑ በድምጽ ማስረጃ ጭምር መጋለፁ ይታወሳል፡፡” ብሏል።

የአንድነት የራት ምሽት በቶሮንቶ ከተማ

ማን ይናገር የነበረ….. የታኅሣሡ ግርግር እና መዘዙ!

$
0
0
(በሰሎሞን ተሰማ ጂ.)
           ዕድል አጋጣሚ፣ ለሰው ልጅ ስትመጣ፣
           መልካምና ክፉ፣ አላት ሁለት ጣጣ !!!
           (ከበደ ሚካኤል፣ “የዕውቀት ብልጭታ”፤)
Man Yinager Yenebere... (Yetahisasu Girgir Ena Mezezu)የታኅሣሥ 1953ቱን (ዓ.ም) “ሥዒረ-መንግሥት” ዋዜማ፣ መባቻና ማግስት ያካተተ መጽሐፍ ታትሟል፡፡ የመጽሐፉ ደራሲ፣ አቶ ብርሃኑ አስረስ ሲሆኑ፣ አሳታሚው ደግሞ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ ነው፡፡ የመጽሐፉ ርዕስ፣ ማን ይናገር የነበረ…..፣ የታኅሣሡ ግርግር እና መዘዙ የሚሰኝ ሲሆን፣በ2005 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ አበባ ላይ ታትሟል፡፡  ይኼንን የሚያህል ቁምነገረኛ መጽሐፍ በ144.00 (አንድ መቶ አርባ አራት) ብር ገዝቶ ቁምነገር መዝረፍ ያጓጓል፡፡ ገጽ በገጽ ሲገልጡት ከ እሰከም ስለሌለው ነፍስን በሃሴት ያጭራል፡፡ አንድ ጊዜ ብቻ አንበውት የማያልቅ ሃተታ የያዘ ድንቅ ድርሳን (Masterpiece) ነው፡፡ ድርሳኑን ደጋግሞ ማንበብ እውነትን የበለጠ ማወቅ ነው፡፡ “ድንቅ የሆነ ድርሳን” ነው ያልኩት ለማጋነን አይደለም፡፡ በእርግጥም፣ ውብ ነው! እጹብ ድንቅ ነው!….
ይኼው ልንገመግመው የመረጥነው መጽሐፍ እጅግ ከፍ ያለ የዋጋ የሚሰጠው፤ የነገረ-መረጃ (Intelegenece)፣ የወታደራዊ፣ የፖለቲካ፣ የሕግ፣ የታሪክ፣ የንግድ፣ የማህበራዊ ሳይንስና የግብረ-ሠናይ ይዘት ያለው ሥራ ነው፡፡ እንደሚታወቀው፣ በሀገራችን የነገረ-መረጃ (የስለላ-ነክነት) ያላቸው መጽሐፍት ቁጥር እጅግ በጣም አናሳ ነው፡፡ ያሉትም ትቂት መጽሐፍት ቢሆኑ የትርጉም ሥራዎች ናቸው፡፡ ለዚያውም ደግሞ የአቶ ማሞ ውድነህ ጥረቶች ናቸው፡፡ ይህም የሆነው በሁለት ምክንያቶች ነው፡፡
አንደኛ፣ የደኅንነት (የመረጃ) መሥሪያ ቤቱ ኃላፊዎቹ በተከታታይ ሕይወታቸው በምስጢራዊ አኳኋን በማለፉና የሚያውቁትን ምስጢራዊ መረጃ ሊዘግቡት ባለመቻላቸው ነው፡፡ በጃንሆይ ዘመን የነበሩት የደኅንነት መሥሪያ ቤት ሃላፊዎች በሙሉ በሰው እጅ አልፈዋል፡፡ አቶ መኮንን ሀብተ ወልድ ዋናው ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ሌ/ኮለኔል ወርቅነህ ገበየሁም ቢሆን ተታኩሶ ነው የሞተው፡፡ ኮ/ል ዳንኤል ደግሞ በሻለቃ ዮሐንስ አራት ኪሎ ቤተ-መንግሥት ውስጥ (ከነሰናይ ልኬ ጋር አንድ ቀን  ነው) የተገደለው፡፡ የደርግ  ዘመን፣ ለረጅም ጊዜያት የደኅንነትና የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር የነበረው ኮ/ል ተስፋዬ ወልደ ሥላሴም ቢሆን፣ ከ21 ዓመታት እስር በኋላ ሊለቀቅ ቀናት ሲቀሩት መሞቱ ተሰማ፡፡ ከርሱም ቀጥሎ ኃላፊነቱን የተቆናጠጠው “ተጋዳላይ” ክንፈ ገ/መድኅን በግንቦት 4/1993 ዓ.ም በጎልፍ ክለብ ተገደለ፡፡ እነዚህ ሁሉ ክስተቶች ተደማምረው፣ የኢትዮጵያን የደህንነት መሥሪያ ቤት የሚመለከቱ መረጃዎች ከኃላፊዎቹ ጋር ተቀበሩ፡፡ የኃላፊዎቹንም ፍጻሜ ያዩት የመረጃ መሥሪያ ቤቱ ሠራተኞች “ጎመን በጤና” ብለው እንዲታቀቡ ጥላውን አጠላባቸው፡፡
ሁለተኛውም ምክንያት ከባህላችን ጋር የተቆራኘ ነው፡፡ በብዙዎቹ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰቦች አኗኗር ውስጥ “አይተኻልን?-አላየኹም!” ሰምተኻልን?-አልሰማኹም!” በል የሚል የመረጃና የደኅንነት መግቻ ጥብቅ ሕገ-ድንብ አለ፡፡ ይህ ሕገ-ደንብ ከማንም በላይ የሚጠብቀው የተጠያቂውን ግለሰብ ደኅንነት ነው፡፡ “ሰውን ማመን ቀብሮ ነው!” ያለችውን ቀበሮ ኢትዮጵያዊት ሳትሆን አትቀርም፡፡ “…ልቡ ዘጠኝ፣ ሰምንቱን ሸሽጎ አንዱን አጫወተኝ!” የተባለው ተረት ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ሳይሠራ አይቀርም፡፡ ያም ባይሆን፣ ብዙዎቹ “ምስጢር፣ የባቄላ ወፍጮ አይደለም” ብለውም የሚያምኑ በመሆናቸው፣ “አይተው-ላለማየትና ሰምተውም-ላለመስማት” ከፍተኛ ጥንቃቄ ያደርጋሉ፡፡ በዚህም የተነሣ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ለበርካታ ዘመናት ያህል፣ ምስጢር-ጠባቂነት የግለሰቦች ባህሪ ከመሆንም አልፎ የወል ባህልም ለመሆን ችሏል፡፡
ወደዋናው ትኩረታችን እንመልስ፡፡….“ማን ይናገር የነበረ…..የታኅሣሡ ግርግር እና መዘዙ”፣ የተሰኘው መጽሐፍ ደራሲ ዋናው የትምህርት ጥናታቸው ኤኮኖሚክስ ነው፡፡ በ1951 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የኤኮኖሚክስ ዲግሪያቸውን በኦክስቴንሽን እያጠኑ ሳለ ከሻለቃ ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ተዋወቁ፡፡ ሁኔታውን እንዲህ ያስታውሱታል፣ “በወቅቱ የምሰራው በአሜሪካን የማስታወቂያ ክፍል (USIS) ነበር፡፡ ደቡብ የመን ደርሶ የመጣውን ጓደኛዬን አዲስ መጽሐፍ ገዝቶ አምጥቶልኝ ነበር፡፡  በሥራ ቦታዬ ላይ ፋታ ሳገኝ ለማንበብ ከጽሕፈት ጠረንጴዛዬ ላይ አስቀምጠው ነበር፡፡….የመሥሪያ ቤቱ ዳይሬክተር… በአንባቢነቴ ይደነቅ ነበርና ጠጋ ብሎ አርእስቱን ቢመለከት “ዳስ ካፒታል” የሚል ሆኖ ያገኘዋል፡፡” በዚህም ሳቢያ አቶ ብርሃኑ በኮሚኒስትነት ተጠርጥረው ወደሕዝብ ፀጥታ ጥበቃ መሥሪያ ቤት ይወሰዳሉ፤ ሻለቃ ወርቅነህም ዘንድ ይቀርባሉ (ገጽ-18)፡፡ (መግቢያችን ላይ የተጠቀምናት፣ “እድል አጋጣሚ፣ ለሰው ልጅ ስትመጣ” የምትለው የከበደ ሚካኤል ስንኝ በትክክል ደርሶባቸዋል፡፡) ደራሲው ከተጠረጠሩበትም የኮሚኒዝም ስርፀት ጣጣ ነፃ ቢወጡም ቅሉ፤ ወደUSIS ተመልሰው እንዳይሠሩ ይደረጋሉ፡፡ ከዚህም ጊዜ ጀምሮ፣ ከኤኮኖሚክስ ጥናታቸው ልቆ የነገረ-መረጃ ሥራቸው ጨምሯል (ገጽ-19)፡፡
“መረጃ አይናቅም፤ አይደነቅም!” በሚለው መሠረታዊ የነገረ-መረጃ ንድፈ-ሃሳብ የሚያምኑት ደራሲ ብርሃኑ አስረስ፣ ሴራውን (መፈንቅለ-መንግሥቱን)ና በሀገሪቱ ውስጥ የነበሩትን የኤኮኖሚ፣ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊና የአስተዳደራዊ ኩነቶች በገለልተኛነት ለመተንተን ያደረጉት ጥረት የሚደነቅ ነው፡፡ የስዒረ-መንግሥቱ ጠንሳሾች፣ “በህዝቡ ላይ የመታየውን የፍርድ ጉድለት፣ የአስተዳደር በደልና የኤኮኖሚ ድቀት እያስጨነቃቸውና ሰላም እየነሳቸው ስለሄደ፣ አማራጭ መፈለግ ግድ እየሆነባቸው መጣ” ይላሉ(ገጽ፣ 151)፡፡ ነገር ግን፣ በኅዳር 29/1953 ዓ.ም ንጉሠ ነገሥቱ በሌ/ኮሎኔል ወርቅነህ በኩል የላኳት ቴሌግራም ያለጊዜው እሳት መጫሯን ያትታሉ (ገጽ-151/2)፡፡
በገጽ 81 እና 82 ላይ እንደገለጹት ሁሉ፣ ሻለቃ ወርቅነህን ለለውጥና ለመሻሻል ያነሳሱትን አምስት ምክንያቶች ዘርዝረዋል፡፡ እነርሱም በኮሪያ ዘመቻና በቶኪዮና ሴኡል የህክምና ጉብኝቱ እንዲሁም በሲዊድን ቆይታው ወቅት በገሃድ ያያቸው መሆናቸውን ያብራራሉ፡፡ ከግርማዊነታቸውም ጋር በተለያዩ አገሮች ሲሄድ ባወቃቸው ኩነቶች ተገፋፍቶ እንደሆነም ያወሳሉ፡፡ የኢትዮጵያንና የሕዝቧንም እድገትና ብልጽግና ያጫጨው “የመሬት ስሪት/ፖሊሲው” ጉዳይ መሆኑን ሌ/ኮሎኔል ወርቅነህን ዋቢ አድርገው ያትታሉ (ገጽ-91/2)፡፡ ኮ/ል ወርቅነህ ባቀረበው የመሬት ስሪት/ፖሊሲው ጥናታዊ ማስታወሻ እንደጠቀሰው፣ “የመሬት ይዞታው ጉዳይ አንደጋንግሪን እየገዘፈ መጥቶ መንግሥትን የሚያናውጥ ሕዝብንም የሚያፋጅ ቀውስ እንደሚያመጣ” ማስረዳቱን ያስታውሳሉ፡፡ በአሁኑም ጊዜ፣ “በዓለም ላይ ርስት የለሽ ሕዝብ ያለባት ብቸኛ አገር (ከኮሚኒስት አገሮች በቀር) ኢትዮጵያ ሳትሆን አትቀርም፤” ይላሉ(ገጽ-92)፡፡ አያይዘውም፣ “ሰው በሰውነቱ እኩል ሆኖ የተፈጠረ ስለሆነ፣ የአገሩ የተፈጥሮ ሀብት ከሆነው መሬት ድርሻ ሊኖራ ይገባል፤….” የሚል አቋም የነበራቸውን አፄ ኢያሱ አድያምሰገድን የመሬት ስሪት ደንብ ያቀርባሉ (ገጽ-121)፡፡ አፄ ምሊልክም አዲስ አበባን ሲቆረቁሩ ይዘውት የነበረውን ፍትሀዊ የመሬት ስሪት ደንብ ያወሱና፣ የምኒልክ ሹማምንት ግን “ከሕዝብ ተለይተው መሬት ለነርሱ ብቻ እንደተፈጠረ ወደ ማድረጉ አዘነበሉና ራሳቸውን ብቻ በማበልፀግ የማኅበራዊና የኤኮኖሚያዊ ኑሮውን ደረጃ ልዩነት አሰፉት፤” ሲሉ ይወቅሳሉ (ገጽ-125)::
በመጨረሻም፣ ከበድ ያለና ጥንቃቄን የሚሻ ትንታኔ ለአንባቢያኑ ያቀርባሉ፡፡ “የኢትዮጵያን የመሬት ስሪት ድልድል እንዳጠና ሌ/ኮሎኔል ወርቅነህና አቶ ገርማሜ ንዋይ አዘዙኝ” ይላሉ (ገጽ-119)፡፡ ገርማሜ የኢትዮጵያን የመሬት ወረራ ያመሳሰለው ለመጀመሪያ ዲግሪው መመረቂያ ጽሑፉ ሲያዘጋጅ ካጠናው ከኬንያው የ“ማው ማው” ንቅናቄ ጋር ነበር፡፡ ሆኖም፣ ከላይ የተገለጹትን የአፄ ኢያሱንና የአፄ ምኒልክን የመሬት ስሪት ድልድል ሲረዳ፣ “ድሮ ከነበረው ስሜቱ መለስ” ብሎ እንደነበር ያስታውሳሉ፡፡ ሆኖም፣ “ገርማሜ ነዋይ፣ እነዚህ ከመሬት ባገኙት ኤኮኖሚ ተጠቃሚ የሆኑ ጥቂቶች፣ የፖለቲካ ስልጣኑንም በመጨበጣቸው በሕዝቡ ላይ ይደርስ ለነበረው የአስተዳደር በደልና የፍትሕ መጓደል በዋናነት ተጠያቂ አድርጎ ያቀርባቸው” እንደነበርም አትተዋል (ገጽ-126ና 139)፡፡ በተመሳሳይ ኹኔታም፣ በገርማሜ ታላቅ ወንድም በብ/ጄኔራል መንግሥቱ ነዋይ ይመራ የነበረውንም የክብር ዘበኛ አምርሮ ይጠላው እንደነበር በገጽ-266 ላይ ዘግበዋል፡፡ ገርማሜ እንዲህ አለ፤ “የክብር ዘበኛ… በመፍረሱ ደስ ብሎኛል፡፡…. ያ ሠራዊት ጀግና ነው፡፡ የታወቀ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ላይ የፈለገውን ነገር ማድረግም ይችል ነበር፡፡ ነገር ግን፣ በንጉሠ ነገሥቱ ላይ ያለው ታማኝነት ከፍ ያለ ስለሆነ ሳይዋጋ ቀረ፡፡…. ሠራዊቱ አንድ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተነሳ ሲባል ሄዶ ያፍናል፡፡ ስለዚህ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሆኑ ማንኛውም ሰው (ድርጅት) በተቃውሞ መንቀሳቀስ ወይም የልቡን ተናግሮ ሀሳቡን መግለጽ ስላልቻለ፣ ይህ ሠራዊት ከተበተነ በኋላ ለተቃውሞ እንቅስቃሴ ይነሣሣል፡፡ ዓላማውም ውጤት እንዲያገኝ ይረዳል….፡፡” ከአራት ዓመታትም በኋላ ገርማሜ ነዋይም እንደተነበየው ሆነ፡፡ በ1957 ዓ.ም ጀምሮ የተማሪዎች አመጽ  እየበረታ ሄደ፡፡
አቶ ብርሃኑ፣ ለመጽሐፋቸው ዋና መነሻ የሆኗቸውን ሃሳቦች ያገኙት በድርጊቱ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆናቸው ነው፡፡ ደራሲው፣ እዚህም-እዚያም ተሰባጥረው የሚገኙትን የ1953ቱን ስዒረ-መንግሥት መነሻና መድረሻ “ማን ይናገር?…የነበረ!” እና “የታኅሣሡ ግርግር”ባሉት ሃይለ-ሃሳብ አደላዳይነት በፈርጅ-በፈርጁ ሊደለድሉት ጥረዋል፡፡ ሙከራቸውም ፈሩን ያለቀቀ ነበር፡፡…. በአስተሳሰባቸውና በአቀራረባቸውም የገለልተኛነት ስፍራን ለመውሰድ ተግተዋል፡፡ በመፈንቅለ-መንግሥቱ ሴራ ተሳትፏቸው የተነሣ ለአምስት ዓመታት ያህል ቢታሰሩም፣ የእልህና የስሜታዊነት ጥገኛ ለመሆን አልፈለጉም፡፡ ከዚህም ከዚያም ብለው ጠቃሚ የሆኑትን ሃሳቦችና ነጥቦች ተፈላልገው በማጠናቀር የዐይን እማኞችን ሃቲት ለማካተት ተግተዋል፡፡ ይሁንና፣ ምንም  የገለልተኛነት መንገድን ለመውሰድ ቢሞከሩ እንኳን፣ በአለቃቸው/በወዳጃቸው በሌ/ኮሎኔል ወርቅነህ ገበየሁ  ተጽእኖ ስር ከመውደቅ አላመለጡም፡፡ “የመፈንቅለ መንግሥቱ መሪዎች” የሚለው ምዕራፍ ሥር “ወርቅነህ ገበየሁ (?-1953)” የሚለው ንዑስ-ርዕስ የደራሲውን የሃሳብ አካሄድና የአስተሳሰብ ፈለግ በይበልጥ የሚመሰክር ነው፡፡ ደራሲው ንጉሠ ነገሥቱንና ሌሎችንም ሰዎች የሚያዩት በእነርሱ ዐይን ነው፡፡ ለአብነትም ያህል ገጽ-85፣ ገጽ-92፣ ገጽ-102፣ ገጽ-111/2፣ ይጠቀሳሉ፡፡ በገጽ-145ና ገጽ-342 ያሉትን አተያዮች ደግሞ በብ/ጄኔራል መኮንን ደነቀና በመቶ አ/ በቀለ አናሲሞስ በኩል ነው ያስተላለፉት፡፡ ይኼንንም ያደረጉት ይሆነኝ ብለው ነው፤ ከስሜታዊነት ለመራቅ፡፡
በተጨማሪም፣ ደራሲው በመፈንቅለ መንግሥቱ ተሳታፊ የነበሩትን ዋና ዋና ተዋንያን እስር ቤት ሳሉና ከወህኒ ቤትም ከወጡ በኋላ ተከታትለው በማናገር የተበታተኑትን ምስጢራዊ መረጃዎች አጠናቅረውና አስፋፍተው በመፃፍ አንድ ጉልህ-ፈር ቀደዋል፡፡ ከእንግዲህ ወዲያም፣ የተለያዩ የታሪክ ተመራማሪዎች፣ የፖለቲካ ሳይንስ አጥኚዎች፣ የሥነ-ጽሑፍና የትውን ጥበባት ቀማሪዎች ስለጉዳዩ በየፊናቸው ለመተርጎም የሚያስችላቸውን ግብዓት አግኝተዋል፡፡ ከዚህም ሌላ፣ ምስጢራዊ ሰነዶችና መረጃዎችም እንደምን ሊገኙ እንደሚችሉ መላና ዘዴውን ገልጠዋል፡፡ ለውጥ እንዴት ያለነውጥ ሊመጣ እንደሚችል ተሞክሯቸውንም አካተዋል፡፡ በምዕራፍ 1ና በምዕራፍ 9 ስርም ያሉት ሁለቱ ሃተታዎች ይኼንን የደራሲውን የሕይወት ተሞክሮና ዕጣ-ፈንታ ይተርካሉ፡፡ የሚደንቀው ነገር፣ ደራሲው “እኔ-በዚህ ወጥቼ፣ እኔ በዚህ ወርጄ!” ከሚለው የንፉግ ትችት የራቁ መሆናቸው ነው፡፡
በታኅሣሥ 1953 ዓ.ም የተደረገውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ተከትሎም፣ በስድስት ኪሎ ገነተ-ልዑል ቤተ-መንግሥት አረንጓዴው ሳሎን ስለተገደሉት አስራ አምስት(15) ባለሥልጣናት አሟሟት ልከኛውን መረጃ ይሠጣሉ፡፡ ግድያውን የመራው ገርማሜ ነዋይ እንደነበረና ዋነኛው ነፍሰ-በላም እጩ መኮንን ነጋሽ ድንበሩ መሆኑን ይገልፃሉ (ገጽ-258 እና 266 ይመልከቱ፡፡) ብ/ጄነራል መንግሥቱ ነዋይ፣ “ኧረ ለመሆኑ ሚኒስትሮቹ እንዴት ሆኑ? ፈታችኋቸው? ልዑል ጌታዬስ? (አልጋ ወራሹስ) ማለታቸው ነው፤” ብለው ሲጠይቁ፣ ገርማሜ “እሳቸው እዛው ናቸው፡፡ ለሚኒስትሮቹ ግን የሞት ቅጣት ሰጥተናል፤” እንዳለ ይተርካሉ፡፡ የመጽሐፉም አንኳር ነጥብ ያለው እዚሁ ላይ ነው፡፡ በኮሚኒዝም ስርፀት ከሁለተኛው የእጩ መኮንንነት ኮርስ የተቀነሰው መርሻ ድንበሩና በኮሚኒስትነት ከወላይታ አውራጃ ገዢነቱ የተነሳው ገርማሜ ነዋይ፣ ዜጎችን ያለፍርድ በመግደል ለነሻለቃ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም አርዓያ ሆኑ፡፡ ለሌሎችም “በዲሞክራሲ ካባ ስር፣ የማርክሲዝምና ሌኒኒዝምን ጃኬት” ለለበሱ ነፍሰ ገዳዮች አጽድቆት ሰጡ፡፡
ማጠቃለያ፤
“ማን ይናገር የነበረ…..የታኅሣሡ ግርግር እና መዘዙ”፣ የተሰኘው መጽሐፍ እጅግ የሚደነቅ የቋንቋ

Addis GudayVol 7. No. 178. Addis Ababa. (1)አጠቃቀምና የቃላት አሰካክን የተከተለ ነው፡፡ አልፎ-አልፎ የቀበልኛ ቃላትን ቢጠቀምም እንኳ፣ በግርጌ ማስታወሻ አማካይነት “ፍቻቸው” ተቀምጧል፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያለው ጉድለት በዋናነት አንድ ነው፡፡ እርሱም፣ በአረንጓዳ ሳሎን ውስጥ በነገርሜ የተገደሉባቸው የራስ አበበ አረጋይ፣ የራስ ስዩም፣ የሜ/ጄኔራል ሙሉጌታ ቡሊ፣ የአቶ መኮንን ሀብተ ወልድና የሌሎችንም ባለሥልጣመናት ቤተሰቦች አለማናገራቸው ነው፡፡ ከዓመታት በኋላ፣ እነዚህ የሟቾቹ ቤተሰቦች ስለመፈንቅለ መንግሥቱ ያላቸውን ስሜትና እውቀት ሊያካትቱት ቢችሉ ምንኛ ዕጹብ-ድንቅ ይሆን ነበር፡፡ ከአቶ ብርሃኑ አስረስ አልገፉበትም እንጂ፣ ትልቅ ሙከራ አድርገው እንደነበር አያጠራጥርም፡፡ በ1953 ዓ.ም የፍትሕ ሚ/ር የነበሩትን ደጃ/ች ዘውዴ ገ/ሥላሴንና ብ/ጄኔራል መኮንን ደነቀን ለማነጋገር ያደረጉት ጥረት መልካም ነው፡፡ እጅግም የሚደነቅ ነው፡፡ በሰማኒያ ሦስት ዓመታቸው የተለያዩ ጫናዎችን ተቋቁመው ይኼንን የመሰለ ድርሳን ስላቀረቡልን ለአቶ ብርሃኑ አስረስ ያለኝን ምስጋናና ልባዊ አክብሮት በአንባቢያን ስም ይድረሳቸው እላለሁ፡፡ አንባቢያንም፣ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ዋጋው ተፋፍቆ በእጥፍ ከምትገዙት፣ ዛሬውኑ መጽሐፉን በትክክለኛው ዋጋ “የግላችሁ አድርጉት!” በማለት ወንድማዊ ምክሬን አስተላልፋለሁ፡፡ ለአቶ ብርሃኑም መልካም ጤንነትና ሰላምን እመኛለሁ፡፡ (በተረፈ፣ በቸር እንሰንብት!)

በሳምናታዊው የአዲስጉዳይ መጽሔት ቅጽ 7፣ ቁ. 178 ላይ፣ በነሐሴ 18 ቀን 2005 ዓ.ም የወጣ ነው::

የአንድነቶች ሰላማዊነት ጽናት በባሌ ሮቤ እና በፍቼ ኦሮሚያ! (ግርማ ሞገስ)

$
0
0

ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)

ሰኞ ነሐሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም. (August 26, 2013)

Girma Mogesአቶ ግርማ ሞገስ

አንድነት ፓርቲ ሳይገድል እየሞተ ህገ-መንግስቱን የማስከበር ሰላማዊ ትግሉን አጠንክሮ ዛሬም ወደፊትም ይቀጥላል፡፡” የሚለውን መርሃቸውን አንድነቶች ካስተዋወቁን ከርመዋል። ባለፈው ሳምንት በባሌ ሮቤ እና በፍቼ ኦሮምያ የተተከሉት መረን የለቀቁ አምባገነን አስተዳደሮች እና ደህንነቶች የፈጸሙባቸውን ወደር የለሽ የአንደበት፣ የሳይኮሎጂ እና የአካል ጥቃት በፈገግታ በመቀበል እየሞቱ ሳይገድሉ በሰላማዊ ትግል ህገ-መንግስቱን ለማስከበር ያላቸውን ጽናት ደግመው አሳይተውናል አንድነቶች። አንድነቶች የሚሰብኩትን የሚፈጽሙ መሆናቸውን ኢትዮጵያ እንደገና ባለፈው ሳምንት ተመልክታለች። የባሌ ሮቤ እና የፍቼ አምባገነን አስተዳዳሪዎች እና ደህንነቶች አረመኔነት አሳፋሪ ነበር። በፍጹም የስልጣኔ አየር የነፈሰባቸው አይመስሉም። ዘመናዊ አስተሳሰብ ለአንድ ቀንም የጎበኛቸው አይመስሉም። ይባስ ብሎ የባሌ ሮቢ እና የፍቼ አስተዳዳሪዎች እና ደህንነቶች ከህጋዊ የመንግስት መዋቅር ውጪ ጸረ-ነፃነት ወረበሎች (ቦዘኔዎች) ያደራጁ ይመስላሉ። ይኽ ጉዳይ ጥናት ሊደረገበት ይገባል።

በባሌ ሮቢ ኦሮሚያ ያየነው አፈና እስከአሁን በሰሜን ኢትዮጵያ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ካስተዋልናቸው አፈናዎች ሁሉ ዘግናኝ ነበር። የመቀሌው አፈና የተፈጸመው የድምጽ ማጉያ በመከልከል፣ የመቀስቀሻ በራሪ ወረቀቶችን በመንጠቅ፣ እና አንድነቶችን በማሰር እንደነበር እናስታውሳለን። የባሌ ሮቤ አምባገነኖች ግን ህውሃት በመቀሌ የፈጸመውን በሙሉ ቢፈጽሙም የአንድነቶችን በታጋሽነት እና በጽናት የታነጸ ሰላማዊ ትግል ሊያቆሙት አለመቻላቸውን ሲገነዘቡ ተራ ማስፈራራት ጀመሩ። ሐሙስ ነሃሴ 16 ቀን 2005 ዓ.ም. የአንድነት ፓርቲ ተወካዮች ከባሌ ሮቤ ከተማ ከንቲባ፣ ምክትል ከንቲባ፣ የፀጥታ ዘርፍ ሃላፊ እና ከከተማው ካቢኔዎች ጋር 3 ሰዓት የፈጀ ውይይት አደረጉ። በዚኽ ውይይት ላይ ነበር የባሌ ሮቢ ባለስልጣኖች “አንድነት ሰላማዊ ሰልፉን ማድረግ አይችልም፤ እኛ ከፍተኛ የሆነ የፀጥታ ስጋት አለብን፡፡ የቀድሞው ጠ/ሚር አቶ መለስ በፓርላማ እንደተናገሩት በአካባቢያችን የአልቃይዳ ክንፍ አለ” የሚል ማስፈራሪያ አዘል በማሰማት ለሰላማዊ ሰልፉ ትብብር መንፈጋቸውን የገለጹት። እሁድ በተቃረበ ቁጥር የባሌ ሮቤ አምባገነኖች ማስፈራሪያ እና ዛቻ ግለቱ እየጨመረ ቢሄድም አንድነቶችን ሊያስቆም አልቻለም። በዚኽን ጊዜ “እሁድ የገበያ ቀን ስለሆነ ሰልፍ ማድረግ አይቻልም። ሰላማዊ ሰልፍ ከተደረገ ደም ይፈሳል።” ማለት ጀመሩ የባሌ ሮቢ ባለስልጣኖች።

 

የአንድነቶችን ጽናት፣ ትዕግስት፣ ሰላማዊነት እና ቁርጠኛነት መስበር እና ሰልፉን ማሰናከል አለመቻላቸውን ሲገነዘቡ የባሌ ሮቤ ባለስልጣናት ቅዳሜ ምሽት ለእሁድ አጥቢያ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች እና አባላትን ካረፉበት ሆቴል በግዳጅ አስወጥተው አገቱ። በዚኽን ጊዜ ነበር የቀሩት አንድነቶች ሰላማዊ ሰልፉ እንዳይደረግ የወሰኑት። የመጣው ይምጣ ብሎ ሰልፍ በመውጣት በመሃይም አምባገነኖች የሰለጠነ የሰላም ትግል ሰራዊት ማስመታት ስህተት ነው። ሰላማዊ ሰልፉ እንዲቀር መደረጉ ትክክለኛ ውሳኔ ነው። በድስፕሊን የታነጹ ሰላማዊ ትግል መሪዎች ገና ዘመቻውን ሲጀምሩ መቼ ማቆም እንዳለባቸውም ጭምረው ያውቃሉ። ይኽ ብስለት ያላቸው ጀግኖች የሚያደርጉት ማፈግፈግ ነው። በዚኽ አይነት ነበር እሁድ ቀን ነሐሴ 19 ቀን 2005 ዓ.ም. በባሌ ሮቤ የታቀደውን የሚሊዮኖችን ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ የታፈነው። በዚኽ አይነት ነበር በባሌ ሮቤ አካባቢ አለ ሲሉን የነበረው ሽብርተኛ የአልቃይዳ ቅርንጫፍ እራሳቸው የባሌ ሮቤ ባለስልጣኖች መሆናቸውን ያረጋገጡልን። ይኽ ሁሉ ሲፈጸም የባሌ ሮቤ ወጣቶች ከአንድነት ፓርቲ ጎን መቆማቸውን ኢትዮጵያችን ልታውቅ ይገባል።

 

ፍቼ ሌላዋ ከተማ ናት። የመጀመሪያው ሁለት አባላትን ይዞ ፍቼ የገባው የሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ቡድን በፍቼ አስተዳደር እና ደህንነት ካድሬዎች ከፍተኛ ድብደባ ተፈጸመበት። የእጅም የእግርም ጉዳቶች ደርሰባቸው ሁለቱ የዴሞክራሲ ሰራዊቶች። አንድነቶች በደረሰው ጥቃት አልተፈቱም። እንዲያውም ጊዜ ሳያባክኑ አዲስ ቡድን ወደ ፍቼ በመላክ ለነሐሴ 19 ቀን ያቀዱትን የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ዘመቻ ለማሳካት ጎንበስ ቀና ማለት ጀመሩ። በዚኽ እርምጃቸው አንድነቶች በማይነቃነቅ ድስፕሊን የታነጹት የሰላማዊ ትግል ሐዋርያት መሆናቸውን ለፍቼ ህዝብ አሳዩ። እየሞቱ ሳይገሉ ህገ መንግስታዊ መብት ለማስከበር ያላቸውን ቁርጠኛነት አንድነቶች አስመሰከሩ። አንድነቶች የሚሉትን የሚፈጽሙ የሰብዓዊ መብቶች አስከባሪ ወታደሮች መሆናቸውን ፍቼዎች በአድናቆት አስተዋሉ። ይኽን ያስተዋሉት የፍቼ ወጣቶች ለአንድነቶች ትብብር መለገስ ጀመሩ። የፍቼ አስተዳደር እና ደህንነቶች ያሰማሩዋቸው ቦዘኔዎች በፍቼ ከተማ የሚገኘውን የአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት ለመስበር ሲሞክሩ የፍቼ ወጣቶች ድርጊቱን በመቃወም ከአንድነቶች ጎን ተሰለፉ። በፍቼ የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍም ቢሆን በአንድነቶች እና በፍቼ ወጣቶች ሰላማዊነት እና ጽናት የተገኘ እንደነበር ኢትዮጵያ በአድናቆት አስተውላለች።

ሶስተኛው የእሁድ ነሃሴ 19 ቀን 2005 የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ዘመቻ እቅድ በአዳማ/ናዝሬት ከተማ ማድረግ እንደነበር ይታወቃል። ይሁን እንጂ የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከአንድነት ፓርቲ ለተጻፈለት ደብዳቤ ነሃሴ 19 በከተማው ስብሰባ መኖሩ እና የኃይል እጥረትም እንዳለበት ጠቅሶ ሰላማዊ ሰልፉን አንድነት ፓርቲ ወደ ጷጉሜ 3 ቀን 2005 ዓ.ም እንዲያዛውር ጠይቋል። አንድነት ፓርቲም የቀረበለትን ጥያቄ መቀበሉን ገልጿል። የአዳማ/ናዝሬት ከተማ አስተዳደር ህገ መንግስታዊ እውቅና ካለው አንድነት ፓርቲ ጋር በዚኽ አይነት ስልጡን እና ተራማጅ መንገድ ከስስምምነት መድረሱ ከባሌ ሮቤ እና ከፍቼ ከተማዎች አምባገነን አስተዳዳሪዎች ፍጹም የተለየ አድርጎታል። ከሁለቱ ከተሞች አስተዳደሮች የአዳማ ከተማ አስተዳደር የተሻለ መሆኑን ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሁን አልመ አስተውሏል። በዚኽ እርምጃው የአዳማ/ናዝሬት አስተዳደር ሊመሰገን ይገባዋል። ሊኮራም ይገባዋል። ኋላቀሮቹ የባሌ ሮቤ እና የፍቼ አምባገነን አስተዳደሮች ሊያፍሩ ይገባል። የሚያስተዳድሩትን ህዝባቸውን በንቀት አፍነውታል። እነዚህን ሁለት ከተሞች ለጉብኝትም ሆነ ለንግድ የሚጓጉ ከተሞች እንዳይሆኑ አድርገዋል እነዚህ አስተዳዳሪዎች። የሚያስተዳድሩትን ህዝብ እና የቀረውን አለም ይቅርታ ሊጠይቁ ይገባል። በእነዚህ እና በመሳሰሉት ከተሞች ላይ ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ የሚፈሰው ገንዘብ ከምንጩ ቁጥጥር ሊደረግበት ይገባል። ከምንጩ ስል ለጋሽ አገሮችን ይጨምራል። ተዳባዳቢነት ዴሞክራሲያዊነት አይደለም! መሃይምነት ነው።

 

ለአንባቢያን፥

 

“እየሞትን ሳንገድል ህገ-መንግስት የማስከበር ሰላማዊ ትግላችንን እንቀጥላለን” የሚለው የአንድነቶች መርህ ከምራቸው እንደሆነ ባልፈው ሳምንትም አስተውለናል። ፍጹም ሰላማዊነታቸው እና የመርህ ጽናታቸው በሚፈጸምባቸው የአካል ድብደባ እንደማይነቃነቅ ፍቼ ላይ አይተናል። በዚኽ ባለፈው የፈተና ሳምንት አንድነቶች መኪና በመከራየት፣ ወረቀቶች በማሳተም፣ ለህክምና ወጪ ባማድረግ እና ለተለያዩ ጉዳዮች ብዙ ወጪዎች እንዳደረጉ መገንዘብ አያዳግትም። ትግሉ የጋራ በመሆኑ  ቋሚ ተመልካች መሆን ያዳግታል። የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል ለምንል በሙሉ የዳር ተመልካች መሆን ያዳግተናል። በባሌ ሮቤ እና በፍቼ በአንድነቶች ላይ የደረሰውን አይተን እና ሰምተን እጃችንን አጥፈን መቀመጥ ህሊናችንን ያዳግተዋል። የዜግነት ሚና መጫውት ያልጀመርን መጀመር፣ የጀመርን ደግሞ መቀጠል አለበን። ተሳትፎዋችንን ማሳደግ አለብን። አንድነቶች አንድም ክፉ ቃል ሳይሰነዝሩ እና ፈገግታ ከፊታቸው ሳይለያቸው ይኽን ሁሉ ስቃይ የሚቀበሉት ለግላቸው ብር ለማካበት እንዳልሆነ ግልጽ ነው። እየሞቱ ሳይገድሉ በአምባገነነኑ መለስ የረቀቀውን ፀረ-ሽብር ህግን ለማሰረዝ እና የኢትዮጵያችንን የፖለቲካ ትግል ባህል ለመቀየር እንደሆነ ልቦናችን ያውቀዋል። ስለዚህም አንድነቶች የጀመሩትን የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ በመቀላቀል ታሪክ እንስራ። የሚከተሉትን በማድረግም አንድነቶች መሰራት የጀመሩትን ታሪክ መቀላቀል እንችላለን።

 

እርዳታ፥ በገንዘብ!

እርዳታ፥ በአሳብ!

እርዳታ፥ መረጃዎች በፍጥነት በማሰራጨት!

እርዳታ፥ ፊርማዎች በማሰባሰብ!

እርዳታ፥ እንደገና በገንዘብ!

 

ፊርማ ለማስቀመጥም ሆነ ገንዘብ ለመላክ ይኽን የአንድነቶች ድረ ገጽ ይጎብኙ፥ www.andinet.org

 

 

በሐውዜን ከተማ የህዝብ ተወካዩ ህዝብ እያስፈራራ ነው

$
0
0

-ከአብርሃ ደስታ (መቀሌ)

Abrham Destaበሐውዜን ከተማ እየተፈፀመ ያለው ያስተዳደር ብልሹነትና የልማት አድልዎ የህዝብ ቁጣ ከቀሰቀሰ ሰንብቷል። ሐውዜን የከተማነት ደረጃ ተነፍጓታል። ህዝቡም ከወረዳ አስተዳደር ጀምሮ እስከ ዞን፣ ክልልና ፌደራል መንግስት ድረስ የልማት ጥያቄውን ያስተጋባ ቢሆንም አግባብ ያለው መልስ የሚሰጥ የመንግስት አካል ግን ፍፁም አልተገኘም።

ጥያቄውና መነሳሳቱ ቀጥሏል። በጉዳዩ የሐውዜን ወረዳ ባለስልጣናት በሁለት ተከፍሏል፤ (1) የወረዳው ስራ አስፈፃሚ አባላትና (2) የወረዳው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት። የስራ አስፈፃሚዎቹ ቡድን አቶ አሕፈሮም ወ/ገብርኤል በሚባል የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን የህዝቡ ጥያቄ ‘የጠላቶች ፖለቲካዊ መነሳሳት ነው’ በሚል ሰበብ የወረዳው ህዝብ በማስፈራራት፣ በማሰርና በጥቅማጥቅም ለመደለል በመሞከር የልማት ጥያቄው ለማዳፈን የሚጥር ነው።

የወረዳው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት ግን የሐውዜን ህዝብ እያነሳው ያለው የልማት ጥያቄ አግባብነት ያለውና አስቸኳይ መፍትሔ የሚሻ ጉዳይ መሆኑ አስረግጠው የሚናገሩ ናቸው። በዚህ አቋማቸው ምክንያት የወረዳው የህዝብ ተወካዮቹ ‘ዓረና የላካቸው ጠላቶች’ ተብለው ተፈርጀዋል። (‘ዓረና’ እየተባሉ ያሉ ሰዎች ህወሓትን ወክለው የተመረጡ የህወሓት አባላት ናቸው)።

ስራ አስፈፃሚዎቹ ለምክርቤት አባላቱ ያስፈሯሯቸዋል፤ ከሓላፊነታቸው ሊያባርሯቸውና ሊያስሯቸው እንደሚችሉ ይነግሯቸዋል። በሐውዜን ሁሉ የተገላቢጦሽ ነው። በመርህ ደረጃ ከፍተኛ ስልጣን ያለው አካል ስራ አስፈፃሚ ሳይሆን ምክርቤት ነው፤ ምክንያቱም የምክርቤት አባላቱ ህዝብ ይወክላሉ፣ የህዝብ ተወካዮች ናቸው። ታድያ ስራ አስፈፃሚዎች ካስፈራሯቸው ምን ዋጋ አለው?

የህዝብ ተወካዮቹ (ቢያንስ በመርህ ደረጃ) የመንግስት አካላት ናቸው። ስራ አስፈፃሚዎቹ ግን በገዢው ፓርቲ የተመለመሉ የፖለቲካ ሹማምንት ናቸው። ተወካዮቹ ጥያቄው ሲደግፉ የፖለቲካ ሹመኞቹ ግን ‘ጉዳዩ የፖለቲካ ውሳኔ’ በመሆኑ ህዝቡ ጥያቄውን እንዲያቆም ጥረት ያደርጋሉ።

የወረዳው ህዝብ ተወካዮች ለጥያቂያቸው መልስ ባለማግኘታቸው የወረዳው የፌደራል ምክርቤት (ፓርላማ) ተወካይ ጠርተው ለማነጋገር ወሰኑ። የወረዳው ህዝብ ወክሎ በፓርላማ የተቀመጠው ሰው የወከለውን ህዝብ የመልካም አስተዳደርና የልማት ጥያቄዎች ማንፀባረቅ እንዲሁም መፍትሔ ማፈላለግ ሕገ መንግስታዊ ግዴታው ነው። ህዝብ ሲቸገር ከህዝብ ጎን መሰለፍ አለበት፤ ምክንያቱም የህዝቡ ድምፅ ለማሰማትና ለመወከል ነው ፓርላማ የገባው።

አቶ አረጋዊ አፅብሃ ይባላል። የድምፂ ወያነ ሰራተኛ ነበር። ህወሓትን ወክሎ የሐውዜንን ህዝብ በፓርላማ ለመወከል በወረዳው ተወዳደረ። አሁን የሐውዜን ህዝብ የልማት አድልዎ ሲደርስበት የፓርላማ ተወካዩ ተጠራ። (ሳይጠራም በራሱ መምጣት ነበረበት፤ ምክንያቱም ህዝቡ ከመወክል ሌላ ህገመንግስታዊ ስራ የለውምና።)

አቶ አረጋዊ ወደ ሐውዜን ቢመጣም ጥያቄው ካነሱ የወረዳው ተወላጆችና የምክርቤት አባላት ጋር ለመነጋገር ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። የፌደራል የምክርቤት አባል ሁኖ ከስራ አስፈፃሚዎቹ የፖለቲካ ሰዎች ወግኖ ጥያቄው ላነሳ ህዝብ በጠላትነት ፈርጆ በከጠር ጣብያዎች (ንኡስ ወረዳዎች) እየተዘዋወረ የጣብያና ቁሸት አስተዳዳሪዎች ህዝቡን ጥያቄውን እንዲያቆም እንዲያስፈራሩት እያስፈራራቸው ይገኛል።

የህዝብ ተወካይ ተብሎ የህዝብን ችግር ከመፍታት ይልቅ ህዝብ የልማት ጥያቄ እንዳያነሳ ማስፈራራት ምን ይሉታል? ደግሞስ ህዝብ የመወከል እንጂ ህዝብ የማስፈራራት ስልጣን ማን ሰጠው? የህዝብ ጥያቄ ማንፀባረቅ ሲገባው የህዝብ ጥያቄ ለማዳፈን ጥረት ያድርግ!? ለመሆኑ ስልጣኑ ምንድነው? ለምንድነው የመረጥነው? ሁላችን መጠየቅ ያለብን ጥያቄ ነው።

አንድ የፓርላማ ተወካይ ስራው በደንብ ካልተወጣ የሚወሰደው እርምጃ ምንድነው? መልሶ መጥራት (Recalling) ከሐላፊነቱ ማባረር። የፓርላማ ተወካዩ ስራ ምንድነው? ህዝብን ወክሎ የህዝብን ጥያቄ በሚመለከተው አካል በኩል መልስ እንዲያገኝ ማድረግ። አሁን ስራው በአግባቡ እየተወጣ ነው? አይደለም። የተሰጠው ሕገመንግስታዊ ሐላፊነት ወደጎን በመተው ተገልብጦ ህዝብ እያስፈራራ ይገኛል። ስለዚህ በሕገመንግስቱ መሰረት ‘የማስመለሻ ትእዛዝ’ (Recalling Claim) ሊሰጠው ይገባል። ካሁን በኋላ የሓውዜንን ህዝብ ወክሎ ፓርላማ ሊቀመጥ አይገባውም። ሌላ የህዝብን ጉዳይ ወክሎ የሚናገር ሰው መመረጥ አለበት።

የሓውዜን ጉዳይ ህወሓትን (የነአባይ ወልዱ ቡድን) በሁለት ሳይከፍል አልቀረም። ጉዳይ በተደጋጋሚ እየተወያዩበት ነው። በህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ አቶ ኢያሱ ተስፋይ የተባለ (የማእከላዊ ኮሚቴ አባል) ‘የሐውዜን ጉዳይ መፍታት ያቃተን ለምንድነው?’ የሚል ጥያቄ ያነሳ ሲሆን የሚያረካ መልስ የሰጠ ባለስልጣን ግን አልነበረም።

በአሁኑ ሰዓት (ከሳምንት በፊት ጀምሮ) የሐውዜን ወረዳና የምስራቃዊ ዞን አስተዳዳሪዎች ከክልል ባለስልጣናት ጋር በጉዳዩ በመቐለ ከተማ እየተወያዩና እየተገማገሙ ናቸው። በግምገማው መሰረት (እስካሁን) የሐውዜን ህዝብ ጥያቄ ለማዳፈን የቤት ስራ ተሰጥቶት የነበረ የምስራቃዊ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ገብረ ከስልጣኑ እንዲባረር ተወስኗል።

አቶ ገብረ የሐውዜንን ጉዳይ እንደምንም ብሎ ማስቆም እንዲችል ታዞ የነበረ ቢሆንም ህዝብ ማሳመን አቅቶት ከሐውዜን ኗሪዎች ጋር ተጣልቶ፣ ህዝቡን ሰድቦ፣ ስብሰባ ረግጦ የወጣ ሰው ነው።

ደግሞስ ህዝብ ልማት አያስፈልገውም ብሎ ለህዝብ ማሳመን ይቻላል እንዴ? ከንቱ ልፋት ነው። ህዝብ ማሳመን የሚቻለው ልማት እንደሚያስፈልገው በመንገር እንጂ ልማት እንደማያስፈልገው በመንገርና በማስፈራራት አይደለም። ብቻ ይገርማል።

የሐውዜን ህዝብ የልማት ጥያቄውን የሚጋራ የራሱ ተወካይ ያስፈልገዋል።

አሜን!

መንግሥት ለተፈጠረው ችግር በአስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግ እንጠይቃለን!!!!

$
0
0

blue party
ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
ፓርቲያችን ሰማያዊ በህገ መንግሥቱ በተደነገገው ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብቱን ተጠቅሞ ለመንግሥት ጥያቄዎችን በማቅረብ ግንቦት 25/2ዐዐ5 ዓ/ም. ታላቅ ህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ አድርጓል፡፡
መንግሥት ላቀረብናቸው ጥያቄዎች በሦስት ወር ውስጥ መልስ የማይሠጥ ከሆነ በተጠናከረና በተደራጀ መልኩ ጥያቄያችንን በድጋሚ በህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ እንደምናቀርብ በግንቦት 25/2ዐዐ5 ዓ/ም. በተደረገው ሠልፍ ላይ ለህዝብ ቃል በገባነው መሠረት ነሃሴ 26/2ዐዐ5 ዓ/ም. በድጋሚ ሰልፍ ጠርተን አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረግን መሆኑን ለህዝብ በልዩ ልዩ መገናኛ ዘዴዎች ገልፀናል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ለሰልፉ በሰላም መጠናቀቅ አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግልን አዋጁ በሚጠይቀው መሠረት ለአዲስ አበባ መስተዳድር ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሰወቂያ ክፍል ጉዳዩን እንዲያውቀው አድርገናል፡፡
ይሁን እንጂ ፓርቲያችን ህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ በጠራበት ግዜና ቦታ ላይ በሌላ አካል ሰልፉ መጠራቱን በትናንትናው ዕለት ነሀሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም በመንግሥት ቴሌቪዥን ዜና ሰምተናል፡፡ በተጨማሪም ለመንግሥት መዋቅር ዜጐች በዚህ ሰልፍ እንዲወጡ በግድ እንዲፈርሙ እየተደረገ መሆኑን ከአዲስ አበባ ኑዋሪዎች አረጋግጠናል፡፡
bluee
ሰማያዊ ፓርቲ አስፈላጊውን የህግ ቅድመ ሁኔታ አሟልቶ ነሐሴ 26/2ዐዐ5 ዓ/ም. በመስቀል አደባባይ የጠራውን ተቃውሞ ሰልፍ ለህዝብ ያሳወቀና አስፈላጊውን ዝግጅት ያጠናቀቀ በመሆኑ ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ በጠራበት ቀንና ሠዓት በሌሎች አካላት የተጠራው ሰልፍ ከመረጃ እጥረት ከሆነ እንዲሠረዝ እየጠየቅን ይህ ካልሆነ ግን ሰማያዊ ፓርቲ በህጋዊ መብቱ የሚያደርገውን የተቃውሞ ሰልፍ ሆን ብሎ ለመረበሽና አቅጣጫውን ለማስቀየስና በዜጐች መካከል ግጭት ለመፍጠር የታቀደ ስለሆነ ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂ መንግሥት መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብና የሚመለከታቸው አካላት እንዲያውቁት በአፅንዖት እንገልፃለን፡፡
በመጨረሻም መንግስት ዜጐችን ያለፈቃዳቸው በማስፈረም ተገደው ሰልፍ እንዲወጡ ማድረግ ህገ ወጥ ስለሆነ፣ በአስቸኳይ እንዲያቆም እንጠይቃለን፡፡
ነሃሴ 21/2ዐዐ5 ዓ/ም.


የሞረሽ አባል ነኝ- ለምን ሞረሽ?

$
0
0

ስለ ሞረሽ ከመናገራችን በፊት የሞረሽን ምንነት መገንዘብ ያስፈልጋል፤ ነገሮችን በቅጡ ከተረዱ ለማማትም መረጃን መሰረት ማድረጉ የተሻለ ይሆናል የሚል እምነት አለኝ፤
ሞረሽ የሚለውን ቃል ከደስታ ተክለወልድ መዝገበ ቃላት ስንፈልገው ከዚህ በታች ያለውን ትርጉም ይሰጣል፤
ሞረሽ (የሌሊት ጥሪ፥ እከሌ ሞተ፦አለፈ ተጎዳ ወዘt) ብሎ ይፈታዋል።
Moving-picture-Ethiopia-flag-flapping-on-pole-with-name-animated-gif
ልክ ስሙም እንደሚያመለክተው ሞረሽ ያለ ረዳት ከኖሩበት፦ እትብታቸውን ከቀበሩበት፦ ከከበሩበት በመንግስት አስተባባሪነት ለሚፈናቀሉት፦ ለሚገደሉት፦ አማሮች ጩኸታቸውን ለማሰማት የተመሰረተ ማሕበራዊ (civic) ድርጅት እንጂ አልፎ አልፎ በአንዳንድ ዜና ማሰራጫዎች እንደሚወራው የአማራ የፖለቲካ ድርጅት አይደለም አላማውም አማራውን ስልጣን ለማቆናጠጥ የሚታገልም አይዶለም።
ከዚህ ቀደም መአህድ የሚባል ነፍሳቸውን ይማርና ሕክምና በወያኔ እስር ቤት ተነፍገው በሞቱት በፕሮፌሰር አስራት የሚመራ ድርጅት ነበር፤ ይህ ድርጅት አመሰራረቱ አማራው ከሚደርስበትና እየደረሰበት ከነበረው ጥቃት ለመከላከል እንጂ የአማራን የበላይነት ለማንጸባረቅ አልነበረም፤ ከፕሮፌሰሩ ሕይወተ ህልፈት ማግስት ግን ውስጣቸው በነበረ ሽኩቻ ድርጅቱ ፈርሶ በመትኩ መኢአድ ተቋቁሟል።
ሞረሽን ከመአህድ የሚለየው ታዲያ ምንድን ነው? ለሚለው መልሱ አጭር ነው ይኸውም የፖለቲካ ድርጅት አለመሆኑ ነው፦ ስልጣን ላይ ለመውጣት የሚታገል ቡድን አለመሆኑ ነው፤
በኔ እምነት አማራ የሚባለው ማነው? ለሚለው ጥያቄ መልሱ እንደመላሾቹ ማንነት የተለያየ ትርጉም አግኝቷል፤ እኔ እንደምረዳው አፉን በአማርኛ የፈታ ሁሉ አማራ ነው፤ ሁላችንም እንደምናውቀው ጎዣም፦ ጎንደር፦ ሰሜን ሸዋ፦ ከፊል ወሎ (ጥንት ስሙ ድፍን ወሎ ቤተ አምሐራ) በአማራነት ይታወቃሉ ስማቸው ግን አማሮች ሳይሆን ጎዣሜ፦ጎንደሬ፦ ወሎዬ፦ መንዜ ወዘተ በመባል ነው።
“እንደ ወያኔና መሰሎቹ ቲኦሪ ግን “አማራ ” የሚለው ቃል፦ አማርኛ ቋንቋ በሚነገርባቸው አካባቢዎች ውስጥ የሚኖረው አማርኛ ተናጋሪ ሕዝብ በሙሉ በአንድ ላይ ሁኖ የሚታወቅበት መለያ ነው፤ ወያኔና መሰሎቹ……የሚሰጉትን ሕዝብ በመነጠል ለማጥቃት የሚያስቸልን ስልት ለመንደፍ ከማሰብ የተከተለ ትርጉም ነው። እንዲህ አይነቱ አካሄድ ደግሞ በወያኔና በኦነግ ዛሬ የተጀመረ አይደለም። በተለያዩ ግዜያት ኢትዮጵያን ለማጥቃት የመጡ የውጭ ሃይሎች በሙሉ ሀገሪቱን ለማዳከምና ለመከፋፈል ሲሉ በነደፏቸው ስልቶች ውስጥ ማእከላዊ ስፍራን ይዞ ይገኝ የነበረ ነው። የኢትዮጵያዊነት እና የአማራነት መለያዎች ህብር ከዘላለም ቁምላቸው gve 54″
ህዋሃት እንደ ትልቅ ጠላት የሚያያቸው ታላቁ አጼ ምኒሊክ የጦር መሪዎቻቸውን ስናይ (ደጃዝማች መሸሻን፦ ደጃዛማቸ ባልቻን፦ ራስ ጎበናን፦ ራስ አሉላን፦ ፊታውራሪ ሀብተግዮርጊስን ወዘተ) አንድ ያደረጋቸውና በሹመት ያሳደጋቸው ኢትዮጵያዊነት እንጂ ጎሳቸው አልነበረም። ዛሬ በወያኔ ዘመን ከዋኖቹ 25 ታላላቅ ጀኔራሎች 20 ትግሬዎች ናቸው፤ የየከፍለ ጦሩ ዋና አዛዦች በሙሉ ትግሬዎች ናቸው።
ሲገዛ የኖረው ጨቋኝ አማራ እየተባለ በወያኔና በመሰሎቹ የሚወራው ፤ ለምሳሌ የመጨረሻውን የኢትዮጵያ ንጉስ ተፈሪ መኮንንን ስንመለከት በእናታቸው አባት ኦሮሞ ሲሆኑ በእናታቸው እናት ደግሞ ጉራጌ ናቸው፤ አባታቸውን ስንመለከት ራስ መኮንን አባታቸው ኦሮሞ ሲሆኑ እናታቸው ደግሞ አማራ ናቸው፤ ስለዚህ ከራስ ተፈሪ አማራነት ኦሮሞነታቸው ያመዝናል፤ በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አማሮች አማርነታቸው አፋቸውን በአማርኛ በመፍታታቸው እራሳቸውን ከአማራ መመደባቸው ነው፤ ይህ ደግሞ ምንም እንኳን በጎሳ እራሳቸውን ላደራጁ ባይመቸም የግለሰቦች መብት ነው፤ የኔም አማራነት ከንደዚህ አይነቱ የተለየ አይዶለም።
በመጀመሪያ ደረጃ ኢትዮጵያዊ ነኝ፤ የተቀረው ከዛ የሚከተል ነው፤ እንደ ሰው እንደ ሰብአዊ ፍጡር የህዋሃት መንግስት ትግል ከጀመረበት ግዜ አንስቶ እስከዛሬ በተለይ በአማራው ላይ የሚያካሄደው የጠላትነት ዘመቻ ይህንን አዲሱን አመለካከቴን እንድይዝ አስገድዶኛል።
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ስለ ኢትዮጵያዊነት ይህንን ይላሉ “ኢትዮጵያዊነት ብዙ የተለያዩ ህብረተሰቦች የተዋሃዱበት አካል መሆን ነው፤ ኢትዮጵያዊነት ከጎሰኝነት በላይና ውጭ የሆነ አጠቃላይ ማንነት ነው፤ ገጽ 31 ኢትዮጵያ ከየት ወዴት”
ስልጣን ላይ የወጣው መንግስት ስለ አማሮች እንዲህ ያስባል “የአማራ ገዢ መደቦች የትግራይ ሕዝብ ጠላቶች ናቸው፤ ታሪካችንና ቅርሶቻችንን ያጠፉት አማራዎች ናቸው፤ ለድህነትና ለስደት የዳረጉን አማራዎች ናቸው፤ በአማራ የተወሰዱት እንደ ወልቃይት ጸገዴ፦ሑመራ አሉ ውሃና ሌሎች የትግራይ መሬቶች እናስመልሳለን ታሪክ አጉዳፊው ገጽ 71 ከገሰሰው እንግዳ” ታጋይ ገሰሰ ውስጥ አዋቂና የወያኔ የትግል አጋር የነበሩ በመሆናቸው ወያኔን ጠንቅቀው ያውቃሉ፤
በተባለውም መሰረት ከአማራው ላይ የተጠቀሱት ቦታዎች ተወስደው ወደ ትግራይ ተደምረዋል፤ አማራውንም ጨቋኝ ብሎ በመሰየም በሌሎች ጎሳዎች ያለ ተከላካይ እንዲመታ አድርገዋል፤ ዛሬ በአሜሪካ ከሕዝብ በዘረፉት ብር ነዳጅ ጣቢያ ከፍተው የተንደላቀቀ ኑሮአቸውን የሚመሩት ታምራት ላይኔ ህዋሃትን ወክለው በምስራቅ ኢትዮጵያ አማራውን ካስጨፈጨፉት አንዱና ዋንኛው ናቸው።
አማርኛ ተናጋሪውን ወገን በጠላትነት መድበው ጨቋኝ ብሔር ይሉታል፤ ሌሎቹ ሁሉም በጀምላ ተጨቋኝ ብሔሮች ሆነዋል።
የአማራውን ቁጥር ለመቀነስ በሚደረገው ትግል ለሌላ በሽታ መከላከያ ነው እየተባለ ሴቶቸን በአማራው ክልል ብቻ በግዳጅ የእርግዝና መከላከያ መርፌ እንዲወጉ ይደረጋል፤ አሉባልታ ሳይሆን በተጨባጭ መረጃዎች ተገኝተዋል የዋሆቹ ሴቶች ለምን መውለድ እንዳቃታቸው ስለማያውቁ በየአድባራቱ ስለት ይሳላሉ፤ ይህ አንድን ዘር ለማጥፋት የሚደረግ በመንግስት የተቀነባበረ ስራ ከዘር ማጥፋት ወንጀል የሚለይ አይደለም፤
እነ መለስ ይላሉ ፕሮፌሰር ጌታቸው ሃይሌ” አማርኛ ተናጋሪውንና የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዩን የሚመነጥሩት ኢትዮጵያን ለማጥፋት በሚሞክሩበት ግዜ አላስኬድ ስላላቸው ነው” በቅርቡ የወያኔ ቁንጮ የሆኑት ስብሃት ነጋ በመኩራራት አማራውንና ኦርቶዶክሱን እንዳያሰራራ አርገን መተነዋል ብለዋል።
ለመንግስትም ያመጣለት ውጤት የአማራው ሕዝብ ቁጥር ማሽቆልቆል ነው በሀዋሃት መረጃ መሰረት የአማራው ሕዝብ ቁጥር በሁለት,ት ሚሊዮን ወርዷል።
ወያኔ ባስተባበረው ጦርነት ሀረርጌ አርባ ጉጉ አማሮች ከነሕይወታቸው ገደል ተከተዋል፦ ቤታቸው ውስጥ ሰዎች እያሉ ተቃጥሏል፦ቆዳቸው እንደእንስሳ ተገፏል፦ ይህ ሁሉ በፊልም የተደገፈ መረጃ አለው፤ በአቶ ሽፈራው ሽጉጤ የተፈረመበት ማዘዣ በቅርቡ ከቤንቺ ማጂ ዞን ጉራ ፋርዳ ህገ ወጥ ተብለው አማሮች መፈናቀላቸው በምትካቸው ደግሞ ቻይኖች፦ ቱርኮች፦ አረቦች እየተጠሩ መሬት ይታደላሉ; ይህ መፈናቀል በዚህ አላበቃም ወደሌሎች ቦታዎችም ተዛምቷል። ቤንሻንጉል ጉምዝ ተመሳሳይ ግፍ ተፈጽሟል።
ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ ወይም በህጋዊ መንገድ ሀገሪቱ ዉስጥ የሚገኝ የዉጭ ዜጋ በመረጠዉ የሀገሪቱ አካባቢ የመዘዋወርና የመኖርያ ቦታ የመመስረት እንዲሁም በፈለገዉ ጊዜ ከሀገር የመዉጣት ነፃነት አለዉ ይላል የሀገሪቱ ሕገመነግስት ነገር ግን ይህ መብት አማራን አይመለከትም የሚል ስንኝ ባይሰፍርበትም በመካሄድ ላይ ያለው ግን የአማራውን ቦታ ከሕግ ውጪ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚኖሩ የውጭ ዜጎች ነው።
እንግዴህ ይህን ሁሉ ከላይ ያሰፈርኩትንና ሌሎች ያላሰፈርኳቸውን በአማራው ላይ የሚደረገውን ግፍ በራሴ ላይ ካልመጣ አያገባኝም ማለት ስለአላስቻለኝ ሞረሽን ለመተባበር ተነስቻለሁ፤ አማራ ባትሆኑም እንደሰብአዊ ፍጡር አንድ ሰው አማራ ስለሆነ ብቻ ይሄ ሁሉ ተዘርዝሮ የማያልቅ ግፍ ሊፈጸምበት አይገባም ብለን ኢትዮጵያውያን በሙሉ በህብረት ልንነሳ ይገባል፤ ወያኔ አማራን የጠላው በኢትዮጵያዊነት አቋሙ እንጂ በሌላ አይደለም፤ ይህ አቋም ደግሞ መቼም ፍንክች አይልም።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር
ታዛቢው

“ምን አዲሱ ትውልድ ብቻ የነገውም ዕዳ ውስጥ ተነክሯል”

$
0
0

ከሱሊማን አህመድ/ከለንደን

ወያኔ እንደወትሮው ሁሉ ለሥልጣኑ ማቆያ ወዳጅ ለማፍራት የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ግዛት በድብቅ እየተደራደረ የመሸጡን ተግባር ትልቁ ሥራው አድርጎ ገፍቶበታል። ይህንን አደገኛ የወያኔ ፕሮግራም መላው ኢትዮጵያዊይም ሆነ አለን የሚሉ የፖለቲካ ድርጅቶች (ትንሹም ትልቁም) በቸልታ የሚያዩት አገራዊ ጉዳይ እንዳልሆነ በጣም ግልፅ እየሆነም ነው።
tplf-rotten-apple-245x300
ወያኔ በገፀ-በረከትነት ለሱዳን መንግሥት የሰጠው 1600 ኪ/ሜ ርዝመትና ከ30 እስከ 50 ኪ/ሜ የጎን ስፋት ያለው ለምና ማዕድን ያረገዘ መሬት “እባክህን ድሮ ለእኔ እንዳደረከው ዛሬ ደግሞ ለጠላቶቸ መከታ፣ ከለላና መተላለፊያ እትሁንብኝ” ብሎ የሰጠው ገፀ-በረከት ብቻ ሳይሆን ብዙዎቻችን እንደምንገምተው ዶላርም ተከፍሎት እንደሆነ አዳዲስ መረጃ እየተገኘ ነው።
ዛሬ ስልጣን ላይ ያሉት ነፍሳት በግልም በቡድንም ሲገመገሙ በፍቅረ-ነዋይ የሠከሩ፣ ራስ ወዳድና ይሉኝታ ቢስ በመሆናቸው ደረቅ ጡቷን እያጠባች ያሳደገቻቸውን ኢትዮጵያን እስክታልቅ ድረስ በካሬ – ሜትር እየሸነሸኑ ለመሸጥ ቆርጠው የተነሱ ለመሆናቸውም በየቀኑ እያየን ነው። ይህን አያደርጉም የሚል ካለ አንድም ሞኝ ነው፣ አለበለዚያም የወያኔ ሽርካ መሆን አለበት።
በጣም አሳዛኙ ነገር ግን ይህን በዓለም ታሪክ ታይቶም፣ ተሰምቶም የማይታወቅ ጭካኔ የተመላበት አገር ሽያጭ ሌላው ቢቀር እንደ – አንድ አገሩን፣ ክብሩንና ኩራቱን እንደሚወድ ማንኛውም የዓለም ሕዝብ ማስቆም አለመቻላችን ነው። በእኔ እምነት ይህን ማድረግ ያልቻልንበት ትልቁ ምክንያት በጥላው ሥር ሕዝብን ማሰባሰብ የሚችል አገራዊ ራዕይ ያለው/ያላቸው፤ ወይም የተሣካለት ገለሰብም ሆነ ድርጅት መውለድ ያለመቻላችን እንደሆነ ዛሬ – ዛሬ ብዙ ኢትዮጵያውያን የምንስማማበት ገሃድ እውነታ ነው ብይ አምናለሁ።
ሌላው፣ የኛ ነገር ፈርዶብን ግራ የተጋባን ሆንና ወያኔ ትናንት ሣይሆን ዛሬ በአገራችንና በሕዝቡ ላይ የፈፀመውንና እየፈፀመ ያለው አገር የመሸጥ ዘመቻ አዕምሯችንን ክፉኛ አቁስሎት “እህህ” እያልን ቁስላችንን በማስታመም ላይ እያለንና ይኼው ከፍተኛ ቁስል ሳያገግም ሌላ አዕምሯችንን ቀስፎ የሚይዝ የተንኮል መላ እየፈጠረ የኅሊና እሥረኞች ሆነን በየጓዳችን እየተብተከተክን እንድንደበቅ ማድረግ መቻሉ ነው።
ከዚህ አንፃር የወያኔ ትልቁ መሣሪያው፣ ከሕዝብ በጉልበት፣ ከአገር ሽያጭና ከፈረንጆች በድርጎ በሚያገኘው ገንዘብ፣ ለሆዳቸው ያደሩና ለማጭበርበሪያ ያህል ትንሽ ፊደል የቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ምንደኞችን ቀጥሮ በሐቀኛና ቁርጠኛ የኢትዮጵያ ልጆች መሀከል የዓላማና የተግባር አንድነት እንዳይፈጠር ሣይታክቱ የሚሠሩ ባንዳዎችን በማሠማራት ነው። ለመከፋፈሉ ዘመቻ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን በገንዘብና በኢንቨስትመንት ሽፋን የአገሪቱን ጥቅም አሳልፎ በመስጠት በሚገዙ ተሰሚነት ያላቸውን ምዕራባውያን ባለሥልጣናትን፣ ጋዜጠኞችን፣ የፓርላማ አባላትን፣ ልዩ – ለዩ ባለሙያዎችና ሀብታም ነጋዴዎች አማካይነትም የሚከናወን ነው።
ወያኔ በነዚህ አገር በቀልና ፀጉረ – ልውጥ አጭበርባሪዎች አማካይነት እየፈፀመ ያለውን አገር የመሸጥ ዘመቻ አሣሦቦት በፅናት የሚቃወም፣ በትግል አጀንዳው ውስጥ አካቶ ሕዝብን የሚያስተባብርና የሚመራ የፖለቲካ ድርጅት እስከአሁን ያለመኖር ጉዳይ ወያኔን ያለሥጋት የሚፈነጭበት አገርና ሕዝብ ያገኘ ዕድለኛ ድረጅት አድርጎታል።
ወያኔ የኢትዮጵያን 1600 ኪ/ሜ ርዝመትና ከ30 -50 ኪ/ሜ የጎን ስፋት ያለው ለም መሬት ለሱዳን በርካሽ ሲሸጥ ሕይዎታቸውን ድንበራቸው ላይ ለማሳለፍ ቆርጠው ከተነሱ ጥቂት ገበሬዎችና ደባውን ለሕዝባችን በተከታታይ መግለጫው ለሕዝብ ይፋ ካደረገው የኢትዮጵያ ድንበር ኮሚቴ በስተቀር ሌሎቻችን ምን መሠረታዊ ሥራ ሠራን? ስለመሬታችን መሸጥስ የተቆጨን ስንቶቻችን ነን? ለትውልድ እያካበትን ያለውንስ አበሣ የምንገነዘብ? ይቅርታ ይደረግልኝና በጣም ጥቂቶች ነን!!
ለሱዳን ተገምሶ ስለተሸጠው አገር መቃወም ቀርቶ ስለመሸጡም ገና ሳናውቅ ወያኔ ከቀረው የኢትዮጵያ ግዛት 1/3ኛውን ከነውሃው ለሕንድ፣ ለቻይና ለሣዑዲና ለሌሎች በብሣና ሥር ውል ማንም ሳያውቅ በሚስጥር መሸጡን፣ የሽያጩንም ገንዘብ በደቡብ መሥራቅ እስያ ባንኮች በመለስ ዜናዊ ስም በተከፈተ የባንክ ሂሣብ ታጭቆ እያቃሰተ ስለመሆኑ እየሰማን እኛ ኢትዮጵያውያን ምን አልን? የፖለቲካ ድርጅቶችስ? መምራት የሚገባቸው ምሑራንስ? ምንም! ጉዳዩ በሁለተኛ ደረጃ እየታየ።
ይሀን በዘዴና ባለማቋረጥ በሚደረግ ትግል ወያኔን ከወንጀል ድርጊቱ ትንሽ እንኳን ሰቅጠጥ የሚያደርግ እርምጃ መውሰድ ቀርቶ ገና አውርተን ሳንጨርስ የዛሬውም የነገውም ትውልድ ሕይዎቱን አሳልፎ እንዲሰጥ የሚጠይቅበትን ትልቅ አገራዊና ትውልዳዊ ጉዳይ ማንም ሳያውቅ፣ ማንም ሳይመክርበት ሌላ የቤት ሥራ ይዞ ከተፍ አለ።
የኢትዮጵያን ለም መሬት፣ ታይቶ የማይጠገብ ውብ ሸለቆና ሸንተረር፣ ማዕድንና ውሃ ባለቤት እንደሌለው ለድርቡሽ አሣልፎ የሰጠ ወያኔ፣ የሽሬን፣ የሽራሮን፣ የተከዜን፣ የዓዲያቦንና የባድመን፣ የዋልድባንና የበረሃሌን ፖታሽ አሳልፎ የሰጠ ወያኔ፣ የአሰብን ወደብ ለሸዓቢያ ሸጦ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ለጂቡቲ የሚሰጥ ወያኔ (ከወደቡ ገቢ ወያኔ ሼር አለው) ዛሬ ማንንም ሳያማክር ከድሆች ኢትዮጵያውያን በጉልበት እየነጠቀ፣ አገርንና ሕዝብን እያስራበ ትልቅ ግድብ እገነባለሁ ብሎ ተነሣ። “ትንሣኤ ግድብ”። አሳፋሪው ጉዳይ ወያኔ ይህንን ሲያደርግ የጠየቀም ሆነ በፅኑ የተቃወመ ያለመኖሩ ሳይሆን፣ ግማሻችን ደጋፊ፣ ግማሻችን ተቃዋሚ ሆነን ቁጭ ማለታችን ነው።
በዚህም ወያኔ በመበራታቱ የደገፈውን ብር/ዶላር አምጣ ለማለት፣ የተቃወመውን ወይንም ትንሽ ያንገራገረውን በብሔራዊ ስሜት አልባነትና በሐሞተ ፈሣሣነት እየከሰሰና አግጣጫ እያሣተ እኛ ስንጨቃጨቅ የቀረውን አገር ለመሸጥ ሰፊ ጊዜ ገዛበት።
የአገራችንን ጉዳይ በቸልታ የምንመለከት፣ ዝንጉዎች፣ የተካፋፈልንና በአንድነት መቆም የማንችል መሆናችንንም በደንብ ስለተረዳ ክፋትና ተንኮል የማያልቅበት ወያኔ ዛሬ ደግሞ አዲስ አገር የመሸጥ አጀንዳ ይዞ ከተፍ ብሏል።
ሰሞኑን ስለዓባይ ግድብ ሥራ መፋፋምና ከጅረቱ አግጣጫ መለወጥ ጋር ተያይዞ ተፈጥሮ የነበረው ግርግር፣ የግብፁ ሙርሲም “ወንዜን በደሜ እጠብቃለሁ” ድንፋታ የሁላችንንም ደም ያንተከተከ አገራዊ ጉዳይ ሆኖ እንደሰነበተ ይታወሳል። ይህ በወያኔና በግብፅ መሪዎች ተዋናይነት ይካሄድ የነበረው ቲያትር ዛሬ ከቶ ምንም እንዳልነበረ፣ ምንም እንዳልልሆነ ጭራሽ ደብዛው መጥፋቱን እየታዘብን ነው። ለምን መሠላችሁ? ወያኔ አገሪቷን ለሌላ ሽያጭ በመደራደር ላይ ስለሆነ ነው። ሌላ የቤትሥራ፣ ሌላ የምናወራው ዜና፣ ሌላ ዕዳ እያዘጋጀልን ነው ማለት ነው። ወያኔ!
ይህ ዓባይን የመገደብ ጉዳይ በድንገት የወያኔ ግንባር ቀደሞ የኢትዮጵያዊ አርበኝነት መግለጫ ሆኖ የቀረበበት ዋና ምክንያት ወያኔ እንደሚያወራውና እንደሚያስወራው ለኢትዮጵያ ሕዝብ ዕድገትና ብልፅግና ራዕይ ኖሮት አስቦ ያደረገው ሣይሆን የግብፅን ሕዝብ በተለይም የአክራሪ ሙስሊሙን እንቅስቃሴ አግጣጫ ለማስለወጥ ሆን ተብሎና ግዜ ተጠብቆ በአሜሪካና በ፳ኤል (በእሥራኤል) አማካይነት ለወያኔ በተሰጠ ትዕዛዝ የሚካሄድ ፕሮጀክት እንጅ (የዓስዋን ግድብ በሶቪየቶች መገደብ ጋር የተያያዘ የቆየ ታሪካዊ ምክንያትም አለው)። የግድቡ ሥራ ሲጀመር ምዕራባውያን በተለይም አሜሪካውያን አይተው እንዳላዩ የመሰሉትም ለዚህ ነበር። ሥራው ከተጀመረና አሜሪካና ፳ኤልም ለግብፅ ማድረስ የፈለጉትን ፖለቲካዊ መልዕክት ካስተላለፉና ግብፅን የመጉዳት አቅማቸውን ካሳዩ በኋላ “ችግሩን በውይይት ፍቱ/ጨርሱ ማለታቸው ወያኔ አደብ እንዲገዛና አርፈህ የሚሰጡህን ተቀበል” ትዕዛዝ ማስተላለፋቸው ፕሮጀክቱ የእነሱ እንጅ የወያኔ ያለመሆኑን ያራጋግጣል።
ስለሆነም ተንበርካኪው ወያኔ ከአሜሪካ በተሰጠው ትዕዛዝ በመልካም ጉርብትና፣ ልማትና የኢኮኖሚ ጥቅም ስም የግድቡን ሥራ አቀዝቅዞ ኢትዮጵያን እስከወዲያኛው የሚጎዳ ሌላ የሚያሥር ስምምነት ከግብፅ ጋር ለማድረግ ላይ ታች ማለት መጀመሩን እያየን ነው። ስለሆነም ነው ዛሬ ያ – ሁሉ ሩጫና ግርግር ቀዝቅዞ፣ ዜናው ከዓለም አቀፍ ሚዲያ፣ ከኢትዮጵያና ከግብፅ ፕራዮሪቲ (ርዕሠ – ዜና) ውጪ እንዲሆን የተደረገውም። በአሁኑ ወቅት የግብፅና ዓለም – አቀፍ ቱጃሮች ከወያኔ ጋር በሚደረግ ሽርክና፣ ለህንድ፣ ለቱርክ፣ ለቻይናና ለሣዑዲ … ወዘተ. የኢትዮጵያ ለም መሬት፣ ውሃና ማዕድን እንደተሸጠ ሁሉ፣ ዛሬም የኢትዮጵያን ለም መሬት፣ ውሃ፣ ደንና ማዕድን ወደፊት ከግድቡ የሚመነጨውንም የኤሌክትሪክ ኃይል በሽርፍራፊ ሳንቲም ለመሸጥ፣ የግድቡንም መጠን ለመቀነስ እየሠሩና እየተደራደሩ ያሉት።
የግብፅ መሪዎችና ቱጃሮች በብዙ ምክንያት ውሃውን ድሮ ሲጠቀሙበት እንደነበረው ሁሉ በፍፁም ባለቤትነት ዝንተ-ዓለም ሊጠቀሙ እንደማይችሉ ይረዳሉ። ውሃም በትነት፣ በተለይም ወደፊት በዓለም ሙቀት መጨመርና በተፈጥሮ ፀጋ መመናመን፣ አብዛኛውን ውሃ በምታመነጨው በኢትዮጵያ አስተማማኝ ዝናብ ያለመኖር፣ የግብፅም እንደ አገር ሊኖራት የሚችለው አስተማማኝ ሠላምና መረጋጋት… ወዘተ. የሚያሳስባቸው ቢሊየነር ግብፃውያንና ሌሎች ሃብታቸውን ለማሸሽና ሌላ አገር ኢንቨስት ለማድረግ እየመከሩና እየሠሩ ሲሆን፣ ከመረጧቸውም አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ነች። አዲስ አበባም በአሁኑ ወቅት በግብፅ ሀብታሞች ተጨናንቃለች።
ይህ ማለት ምን ማለት ነው? ይህ ማለት ኢትዮጵያ ከግብፆች ጋር በመልካም ጉርብትና፣ በሠላምና በጋራ ልማት ስም ወያኔ የሚያደርገው ሕዝብ የማያውቀው፣ ያልመከረበትና ያልተስማማበት ልፍስፍስ ስምምነት አንዴ ከፀደቀና ዓለም – አቀፍ ዕውቅና ካገኘ ለዛሬው ሳይሆን ለነገውም፣ ለተነገ ውዲያውም፣ ቀጥሎ – ቀጥሎ ለሚመጣውም ወያኔም እኛም ትተነው የምንሄድ “የተውልድ አበሣ” ማለት እንደሆነ ግልፅ ነው። መፍትሄውም ዛሬ – ነገ ሳንል በአንድ ሆነን ይህንን የአገር ሽያጭ ማስቆምና ሕገወጥ ነጋዴውንም ማስወገድ መቻል ነው። ይህንን ማድረግ ካልቻልን የወደፊቷ ኢትዮጵያ ምን እንደሚጠብቃት ማሣሠብ ያንባቢዎቼን ዕውቀት መጠራጠር ይመስልብኛልና አላነሳውም።
ወያኔ ጊዜ እየጠበቀ በሚቀይስልን ተለዋዋጭ ተንኮል እየተመራን አንዱን እያነሳን ሌላውን እየጣልን፣ ያለፈውን እየረሣን አዲሱን እያዳነቅን እርስ -በርሣችን ከመነታረክና “የትውልድ አበሣ” ከመሆን እራሣችንን ማዳን ካልቻልን፣ የአገራችን ፖለቲካ መላው እየጠፋ፣ እዳችንም እየከበደ፣ መፍትሄውም ከሰማይ እየራቀ እንደሚሄድ ግን አያጠራጥርም።
ስለሆነም አለን የሚሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ትግላቸውን በያዝ ለቀቅ ሣይሆን በግልፅ አገራዊና ሁሉን አቀፍ እስትራቴጂካዊ ፕሮግራም፣ መሪና አሠባሳቢ መፈከር ነድፈው ሕዝቡን ማስተማር፣ ማሳወቅና (ኢንፎርም ማድረግ) መምራት ተቀዳሚ ዓላማቸውና ትልቁ ሥራቸው መሆን ይገባዋል። ፕሮግራማቸውንም መንደፍ ያለባቸው ይሄኛው እከሌን ያስደስታል፣ ያኛው እክሌን ያስቀይማል – ያስቆጣል ሣይሉ፣ ለጊዜያዊ ታክቲክና ጥቅም ሣይታለሉ ለረጅሙ ግብ ሕዝብን ማዘጋጀት የሚችል አግጣጫ ጠቋሚና አሠባሣቢ ትልም መሆን አለበት።
በመርሐ – ግብራቸው ውስጥም መካተት ካለባቸው ዋናና ቀዳሚ ጉዳዮች አንዱ የኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛትና ዳር ድንበር ከየት እስከየት እንደሆነ የማስቀመጥና ለመጠበቅም ያለባቸውን አደራና ሃላፊነት በግልፅ መያዝ ይገበዋል።
ነገ መምጣቱ ለማይቀር አገራዊ ጉዳይ ፖለቲካዊ ድርጅቶች በቅድሚያ ራሣቸውን ቀጥሎም ሕዝቡን አሠባሣቢ በመሆን መርሐ – ግብር አደራጀተው መጠበቁ ወሳኝና ለሚቀጥለው ሥራቸውም ጠንካራ መሠረት ነው።
ፖለቲካ ድርጅቶችና መሪ ኤሊቶች ይህን መሠረታዊ ጉዳይ ለጊዜያዊ ፖለቲካዊ ጥቅምና መሽኮርመም ወይም ፖለቲካዊ ይሉኝታ ወይም ታክቲክ ወይም በቸልታ የሚያልፉት ከሆነ እንደ ኢትዮጵያ ድንበር ኮሚቴ መግለጫ “አዲሱ ብቻ ሣይሆን የነገውም ትውልድ ከማይሸከመው ዕዳ ውስጥ መነከሩ” አይቀርምና ከአሁኑ አካሄድን ማሣመር ለነገ የሚተው ሃላፊነት አይደለም።

ግልጽ ደብዳቤ ለሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባላት (አማኑኤል ዘሰላም)

$
0
0

አማኑኤል ዘሰላም
amanuelzeselam@gmail.com

 

ነሐሴ  21 ቀን 2005 ዓ.ም
ለተከበሩ ኢንጂነር ይልቃል፣  ለክቡራን ከፍተኛ የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባላት፣ በቅድሚያ ሰላምታዬ ባላችሁበት ቦታ  ይድረሳችሁ!  ጤና ይስጥልኝ።

ለሰማያዊ ፓርቲ አድናቆት አለኝ። የግራዚያኒ ሃዉልትን በመቃወም ያደረጋችሁት ሰልፍን ተከታትያለሁ።  በብዛት ግን ሰው ያወቃችሁ፣ በአዲስ አበባ በጠራችሁት ሰላማዊ ሰልፍ ነዉ። ያኔ ትልቅ ሥራ ነው የሰራችሁት። አኩርታችሁኛል። ብዙ ደጋፊዎችም በአጭር ጊዜ ዉስጥ አግኝታቹሃል።

mailያኔ የጠራችሁትን ሰልፍ አብዛኞቻችን ብንደግፈውም፣ ሌሎች ድርጅቶችን ሳታማክሩ ፣ ሰልፉን በችኮላ መጥራታችሁ ግን ብዙዎችን ደስ አላሰኝም ነበር። ነገር ግን «ማንም ይጥራዉ፣ ማንም ፣ ትግሉን እስከጠቀመ ድረስ መተባበር ያስፈልጋል» የሚል አቋም በርካታ የአንድነት ፓርቲና መኢአድ አመራር አባላት በመያዝ ድጋፍ ሰጧችሁ። መኢአድ በመግለጫ ድጋፉን ገልጸ። በፓርቲ ደረጃ፣ የሥራ አስፈጸማዊ፣ ምክር ቤቱ ተነጋግሮበት ዉሳኔ ለመወሰን 15 ቀናት በቂ ስላልነበረ፣ በኦፈሴል የአንድነት ፓርቲ ድጋፍ ባይሰጥም፣ የፓርቲዉ አመራር አባላት ግን እንደ ኢሳት በመሳሰሉ ሜዲያዎች በመቅረብ፣ የአንድነት አባላትን ደጋፊዎች በሰልፉ እንዲገኙ፣ ሰማያዊ ፓርቲ ለጠራዉ ሰልፍ ድጋፍ እንዲሰጡ ጥሪ አቀረቡ። በአዲስ አበባ 23ቱም ወረዳዎች የሚገኙ የአንድነት አስተባባሪዎች፣ «የሰማያዊ ፓርቲ የጠራዉ ሰልፍ፣ የኛም ሰልፍ ነው» በሚል በየወረዳዎቻቸዉ ቅስቀሳ ሲያደርጉ፣ መፈክሮችን ሲያዘጋጁ እንደነበረም ታውቃላችሁ። የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላትም በሰልፉ ተገኝተዋል። አንድነት ፓርቲ፣ እንዲሁም መኢአድ ለሰማያዊ ፓርቲ ሙሉ ድጋፉቸውን በዚህ መልኩ መስጠታቸው ተገቢና አስፈላጊ ነበር።

የአዲስ አበባዉን ሰልፍ ተከትሎ፣ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል መርህ እንቅስቃሴ ጀመረ። በጎንደርና በደሴ ቅስቀሳ ይደረግ በነበረበት ጊዜ፣  የሰማያዊ ፓርቲ፣ ድጋፉን እንዲሰጥና ከጎንደርና ከደሴ ሕዝብ ጎን እንዲሰልፍ  አንዳንዶቻችን  ጠይቀን።  ከአዲስ አበባ ዉጭ ድርጅታዊ አቅም እንደሌላችሁ እናውቃለን። ነገር ግን ቢያንስ ቢያንስ፣ በመግለጫ ደረጃ ሰላማዊና ህዝባዊን ንቅናቄ በመደገፍ ከጎንደርና ከደሴ ሕዝብ ጎን መቆም ይገባችሁ ነበር። ያንን ግን፣ ተጠይቃችሁም እንኳን፣ አላደረጋችሁም። አንድነት ፓርቲ ከእናንተ ጋር አጋር እንደነበረዉ፣ እናንተ ግን ወገናዊ ምላሽ መስጠት ተሳናችሁ። ከጎንደሩና ከደሴዉ ሰል በኋላ በጂንካ፣ በአርባ ምንጭ፣ በባህር ዳር፣ በፍቼ ሰላምዊ ሰልፎች የተደረጉ ሲሆን፣  በመጨረሻዉ ሰዓት ላይ የአንድነት አመራር አባላትን በማሰርና በማንገላታት ከፍተኛ ጫና ሕወሃትና ኦሕድድ በማድረጋቸው ሰልፎቹ ተላለፉ እንጂ፣ በመቀሌና በባሌ/ሮቢ እንቅስቃሴዎች ተደርገዋል። በነዚህ ሁሉ ከተሞች የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምጹን ለሰላም፣ ለዲሞክራሲን አለነጻነት ሲያሰማ ድርጅታችሁ ድምጹን አጥፍቶ ነበር። በዚህ እዝኜባቹሃለሁ።

የጎንደሩን እና የደሴዉን ሰልፍ ተከትሎ የአንድነት ፓርቲ አዲስ አበባ ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች ሊያደርጋቸው ያቀዳቸውን ሰልፎችና ህዝባዊ ስብሰባዎች ለሕዝብ አሳወቀ። በፕሮግራሙ መሰረት፣ ከበርካታ ሰልፎች መካከል ፣ በአዲስ አበባ መስከረም 5 ቀን፣ በአሶሳና ጋምቤላ ነሐሴ 26 ቀን  ሊደረጉ የታሰቡ ሰልፎች ይገኙበታል።

ብዙዎቻችንን  የገረመን  የአንድነት ፓርቲ ሰልፍ እንደሚጠራ ባሳወቀ በሁለት ቀኑ ፣ በችኮላ  ነሐሴ 26 ቀን በአዲስ አበባ ሰልፍ እንደምትጠሩ መግለጻችሁ ነበር። እየተደረገ ያለው፣  ትግል እንጂ ጨዋታ እንዳልሆነ በማስመር፣  ሰልፉን ከአንድነት ፓርቲ ጋር እንድታደረጉ ጥያቄ አቀረብንላችሁ። ያ ብቻ አይደለም፣  የፖለቲካ ፕሮግራም ልዩነቶችን ባለመኖራቸው፣  ከአንድነትና ከመኢአድ ጋር መዋሃድ የሚቻልበትን ሁኔታ እንድታመቻቹ አበረታታን።

አንድ የአንድነት ፓርቲ አመራር አባልን፣  በዚህ ጉዳይ ላይ ሳነጋገር «እንኳን ሰልፍ ከነርሱ ጋር ለማድረግ፣ እንደዉም የፖለቲካ ፕሮግራሞቻችን አንድ ናቸው። እንዋሃድ ብለን ጠይቀናቸው ፍቃደኛ አልሆኑም» የሚል መልስ ነው የሰጡኝ። በአጭሩ፣ በአንድነት ፓርቲ ዘንድ፣  ከማንም ድርጅት ጋር፣ በጋራ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ አብሮ ለመስራት፣ ሰላማዊ ሰልፎችን  ለማስተባበር ፣ ፍቃደኝነት እንዳለ ነዉ የተረጋገጠልኝ።

 

ነገር ግን ከእናንተ አዎንታዊ ምላሽ ልናገኝ አልቻልንም። «የሚጠየቁት ጥያቄዎች አንድ አይነት ሆነው፣ ለሰልፍ የሚጠራዉ ህዝብ አንድ ሆኖ፣ በሁለት ሳምንት ጊዜ ዉስጥ፣ ሁለት ሰላማዊ ሰልፎች መጥራት ምን ይባላል ? ገንዘብና ጊዜ ማባከን ነዉ» በሚል ብትችሉ አብራችሁ  ከአንድነት ጋር መስክረም 5 ቀን ሰልፍ እንድታደርጉ፣ ካልተቻለ ደግሞ የሰልፉን ቀን ትንሽ ራቅ እንዲል ተማጸንን።

በነሐሴ 26 ቀን በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራት፣ በጋምቤላና በአሶሶ፣ ነሐሴ 26 ቀን  የአንድነት ፓርቲ ሊያደርጋቸው ያቀዳቸውን  ሰላማዊ ሰልፎችና በዚያም የሚኖረው ሕዝብ ጥያቄ በስፋት እንዳይዘገብና ትኩረት እንዳያገኝ የሚያደርግ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ለጋምቤላና ለአሶስ ሕዝብ ክብር እንድትሰጡም ጠየቅናችሁ።

ነገር ግን «አልሰማም፣ እምቢ አሻፈረን» አላችሁ። ግትር ሆናችሁ።  በሰንደቅ ጋዜጣ ላይ የድርጅታችሁ ሊቀመንበር አቶ ይልቃል «ለምን ከሌሎች ድርጅቶች ጋር አብራችሁ አትሰሩም ? » ተብለው ሲጠየቁ «ምን የሚረባ ድርጅት አለህ ብለህ ነዉ ? » የሚል አሳዛኝና አሳፋሪ ከአንድ የፖለቲካ ድርጅት መሪ የማይጠበቅ ምላሽ ነበር የሰጡት። በአሜሪካን ድምጽ ራዲዮ፣  ከማንም ድርጅት ጋር ግንባር፣ ቅንጅት፣ ዉህደት ለመፍጠር  ሰማያዊ ፓርቲ ፍላጎት እንደሌለውም አቶ ይልቃል በድጋሚ አስምረዉበታል። በአጭሩ ሰማያዊ ፓርቲ ለብቻው መጓዝ የመረጠ ይመስላል። በዚህም ምክንያት ሰማያዊ ፓርቲ ከሰላሳ ስምንቶቹ ዉጭ ሊሆን ችሏል።

የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላት፣ «ሰማያዊም ሆነ ማንም ድርጅት፣  ድርጅታዊ ነጻነትና፣ ባመነበትና ባቀደው መንገድ የመንቀሳቀስ መብት አለዉ» በሚል የሰማያዊም ሆነ የሌሎችን ሥራ ላይ አስተያየት መስጠት አልፈልጉም። ሌሎች የሚያደርጉትን  ለነርሱ ትተው፣  በኦሮሚያ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በመቀጠል በሮቤና በአዳማ፣ እንዲሁም በመቀሌ፣ አሶሳ፣ ጋምቤላእንዲሁም አዲስ አበባ  ሰላማዊ ስለፎችን ለማድረግ እየተዘጋጁ  ነዉ። የኢትዮጵያን ሕዝብ፣  በአዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በደቡብ፣ በትግራይ፣ በአማራዉ ክልል፣ በኦሮሚያ ፣ በጋምቤላ፣ በቤኔሻንጉል …እያንቀሳቀሱት ነዉ። ጸጥ ብለው ስራቸውን እየሰሩ ነዉ። በዚህ በርቱ፣ ቀጥሉበት እንላቸዋለን።

 

ድርጅታችሁ በሕዝብ ካልተደገፈ የትም ሊደርስ አይችልም። እንደከዚህ በፊትም  ሕዝቡ በቀላሉ ለፖለቲካ ድርጅቶች ድጋፍ ለመስጠት ፍቃደኛ አይደለም። ሕዝቡ ከፖለቲካ ድርጅቶች የሚጠብቀዉ ነገር አለ። «አንድ የተቃዋሚ ድርጅት ኢሕአዴግን ተክቶ፣ በኢትዮጵያ ዉስጥ ያሉ ልዩነቶችን አጣቦ፣ ያገሪቷን አንድነት ጠብቆ፣ በአገሪቷ ሁሉ ሰላምና መረጋጋትን አስፍኖ አገር ማስተዳደር ይችላል ወይየሚል ጥያቄ ይጠይቃል። ሕዝቡ «ምን ያህል ኢሕአዴግን ይቃወማልየሚል ጥያቄ አይደለም የሚጠይቀው። «ከኢሕአዴግ ይሻላል ወይ ? » የሚል ጥያቄ ነዉ የሚጠይቀዉ። ሕዝብን ለማሰባሰብ የሚችል ድርጅት ደግሞ ሌሎችን የሚያከብር፣ ትሁት መሪዎች ያሉት ድርጅት መሆን ይኖርበታል።

 

እንግዲህ ትህትና ይኑራችሁ እላለሁ። ከአሁን ለአሁን አንድ ሰልፍ ጠራችሁና እራሳችሁን እንደ ግዙፍ ማየታችሁን አቁማችሁ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎትና ጥያቄ እራሳችሁን አስገዙ እላለሁ። በነሐሴ 26 የጠራችሁትሰላማዊሰልፍንሰርዙ። የአዲስ አበባ ሕዝብ በአስራ አምስት ቀናት ዉስጥ ሁለት ጊዜ ሰልፍ ሊወጣ አይገባም። ሰልፍ ለማዘጋጀት ትልቅ የገንዘብ አቅም ይጠይቃል። በመሆኑም ሰልፉን መስክረም 5 ቀን ከአንድነት ፓርቲ ጋር አብራችሁ አድርጉ። በአንድነት ፓርቲና በሰማያዊ ፓርቲ ካስፈለገም ሌሎች ድርጅቶችን ያቀፈ ግብረ ኃይል ተቋቋሞ የመስከረም 5ቱን ሰልፍ ያስተባብር። ይሄን ለማድረግ ትንሽ ጊዜ ካስፈለገም የመስከረም 5 ቱን ሰልፍ በአንድ ወይንም 2 ሳምንታት እልፍ እንዲል ማድረግም ይቻላል።

 

እግርጥ ነዉ ለኢሕአዴግ የሶስት ወራት ጊዜ ሰጥታችሁታል። «ጥያቄያችንን ስላልመለሰ በገባነው ቃል መሰረት በሶስት ወሩ ሰልፍ መዉጣት አለብን» የሚል አስተያየት ሊኖራችሁ ይችላል። እስቲ ልጠይቃችሁ …ከመጀመሪያዉ ሰልፍ በኋላ ያልሰማችሁ ኢሕአዴግ፣ አሁን ለምን ይሰማቹሃል ? እንዳለፈው ጊዜ የአንድነት/መኢአድ አባላትና ደጋፊዎች አይተባበሯችሁም ።  ለምን ለመስክረም 5 ዝግጅት ስለሚያደርጉ። ለሰልፍ የሚመጣዉ ሕዝብም ቁጥሩ ሊያንስ ይችላል። ያ ደግሞ የበለጠ ተቀባይነታችሁን ይሸረሽርዋል እንጂ የሚፈይደው አንዳች ፋይዳ የለም።

 

ይልቅስ  በኢሕአዴግ ላይ የበለጠ ጫና ማሳደር ከፈለጋችሁ፣ በሚቀጥለው ሰልፍ ኢሕአዴግ እንዲሰማ ከፈለጋችሁ፣ ከአንድነት ፓርቲ፣ ከመኢአድ ከመሳሰሉ ጋር እጅና ጓንት ሆናችሁ መስራት ይኖርባቹሃል። የአንድነት ፓርቲ ያለ አንዳች ቅደመ ሁኔታ ከናንተ ጋር ለመነጋገር፣ ሕብረት ለመፍጠር ዝግጁ ነዉ። ከእናንተ ጋር ብቻ አይደለም ከማንም ድርጅቶች ጋር አብሮ መስራት ይፈልጋል። ለዚህም ነዉ ከአምስት አመት በላይ በመድርክ ዉስጥ ሲንቀሳቀስ የነበረዉ። (ይሄን ያህል ዉጤት ባይገኝም)  ለዚህም ነዉ ከመድረክ አልፎ፣ መድረክን ተክቶ፣ ድርጅቶችን በሚስማሙበት ጉዳይ አሰባስቦ ጥሩ ሥራ ሊሰራ ይችላል ብዬ በማስበው፣  በሰላሳ ሰምንቶቹ ዉስጥ ፣ ድርጅቶች በአንድ ላይ ሆነው በአገዛዙ ላይ ጫና እንዲያሳድሩ እየሰራ ያለዉ። ለዚህ ነዉ ዘሃበሻ እንደዘገበዉ ከመኢአድ ጋር ለመዋሃድ እንቅስቃሴ የሚያደርገዉ።

 

እዚህ ላይ አብቃ። ተስፋ አደርጋለሁ ምክሬን እንደምትሰሙ። ሕዝቡ ይከታተላል። ሕዝቡ ሁሉንም ይመዝናል። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቅ ሚና ልትጫወቱ ከፈለጋችሁ ጉዟችሁን በጥንቃቄና በማስተዋል አድርጉ። ትላንት ግዙፍና ተወዳጅ የነበሩ፣ አሁን ግን የተተፉ የተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎችና ድርጅቶች እንደነበሩና እንዳሉም አትርሱ።

 

(ዘግይቶ የደረሰኝ መረጃ የአንድነት ፓርቲ፣  ነሐሴ 26 ቀን ፣ ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ ከመጥራቱ በፊት፣ አስቀድሞ በጋምቤልና በአሶሳ ያቀዳቸዉን ሰልፎችን እንዲሁም በድረደዋ በመሳሰሉ ከተሞች  ሊደረጉ የታቀዱ ሕዝባዊ ስብሰባዎችን ሰርዟል። ይመስለኛል ሰማያዊ ፓርቲ ተገቢዉን የሜዲያ ትኩረት እንዲያገኝ ታስቦ ሳይሆን አይቀርም። ለሌሎች ድርጅቶች ከበሬታ ማሳየት ማለት ይሄ ነው)

የኢህአዴግ ስውር ሴራ በሮቤ ከተማ ተጋለጠ!!! ሐገሪቷን የሚያስተዳድራት ማነው? የባሌ ሮቤ ሰላማዊ ሰልፍ ለምን ተደናቀፈ?

$
0
0

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

 

ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ ማብራሪያ

የሚሊየኖች ድምፅ ለነፃነት ንቅናቄ በአራቱም የኢትዮጵያ ማዕዘናት የነፃነት ድምፅ ማስተጋባት ከጀመረ እንሆ ዛሬ ስልሳ ሰባተኛ(67) ቀኑን ይዟል፡፡ ፓርቲያችን በእዚህ ታላቅ ሕዝባዊ የነፃነት ንቅናቄ መሪር የሆነ ውድ ዋጋ እየከፈለ ድምፅ አልባ ለሆኑት ሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያን ድምፅ በመሆኑ ታላቅ ደስታ ይሰማዋል፡፡

ላለፋት ስምንት ዓመታት ሰቆቃ እና ግፍ በገዢዎቻችን ሲፈፀምበት የኖረው የገጠሩም ሆነ የከተማው ታላቁ ህዝባችን ‹አንድነት ፓርቲአችን አስትንፋሳችን› በማለት  አንድነት ፓርቲ ባመቻቸለት ህዝባዊ ስብሰባዎች እና ሠላማዊ ሠልፎች በነቂስ በመውጣት የታፈነ ብሶቱን በግልፅ በአደባባይ ላይ በማሰማቱ ኢህአዴግ እና ህዝቡ ዛሬም ድረስ ተለያይተው እንዳሉ አንድነት ፓርቲ በማያወላዳ ሁኔታ በሚሊዮኖች ድምፅ ንቅናቄ በህዝባችን መሀል በመገኘት አረጋግጧል፡፡

ኢህአዴግ የቀረው በውሸት እና በሴራ የተሞላ የቅጥፈት ፕሮፖጋንዳ ብቻ መሆኑን ይበልጥ ያረጋገጠልን የባሌ ዞን አስተዳደር እና የሮቤ ከተማ አስተዳደር ያዘጋጁት በሀገር ሽማግሌዎች ስም የተቀነባበረው የእናደራድራችሁ አሳፋሪ ድራማ ለኦሆዴድም ሆነ ለኢህአዴግ ታላቅ ውድቀት ነው፡፡

አንድነት ፓርቲ በባሌ ሮቤ ከተማ ሠላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ህጉ በሚያዘው መሰረት ነሐሴ 13/2005 የሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ደብዳቤ ለከተማዋ አስተዳደር አስገባ፡፡ ጉዳዩን የሚከታተሉት የፓርቲው ተወካዮች ደብዳቤው ከገባ ከ48 ሠዓት በኋላ ወደ መደበኛ ቅስቀሳቸው መግባት እንደሚችሉ ህጉ እንደሚፈቅድላቸው የተረዱት የፓርቲያችን ትንታግ ታጋዮች ጊዜ ሳያባክኑ የተዘጋጀውን የቅስቀሳ በራሪ ወረቀት በከተማ ውስጥ ማሰራጨት ጀመሩ፡፡

ሁኔታውን በቅርብ ሲከታተሉት የነበሩት የፌደራል መንግስት እና የክልሉ መንግስት ከሮቤ ከተማ አስተዳደር ጋር በመቀናጀት አንድነት ፓርቲ ላይ ያጠመዱት ሴራ ለመተግበር የከተማው ከንቲባ አቶ አብዱል ላጥፍ ነሓሴ 13/2005 ለገባላቸው የፓርቲው ደብዳቤ መልስ ያሉትን ነሓሴ 13/2005 ቀን እንደ ተፃፈ ተደርጎ ፓርቲው አላማ ያሉትን ዘርዝረው ነሓሴ 17/2005 ዓ.ም ደብዳቤ ለፓርቲው ተወካዮች ሰጡ፡፡ የተባሉትን ሰበቦች እና ምክንያቶችን በሙሉ አሟልቶ ፓርቲው የእዚያኑ ዕለት በደብዳቤ ምላሽ ቢሰጥም የከተማው አስተዳደር ባለስልጣኖች ከንቲባውም ጭምር ቢሮአቸውን ዘግተው ጠፉ፡፡ መዝገብቤትም ለማስገባት የተደረገው ጥረት በመዝገብ ቤት ሰራተኞች እምቢ ባይነት ሳይሳካ ቀረ፡፡ የአምባ ገነኑን የኢህአድግ ባለስልጣኖችን ነውረኛ ስራ ቀድሞ የሚያውቀው የአንድነት ፓርቲ የተዘጋጀውን ደብዳቤ በሪኮማንዴ በፓስታ ቤት በኩል አንዲደርሳቸው በማድረግ ምንም መፈናፈኛ ሰበብ እንዳያገኙ አደረገ፡፡                                                                                                                            ግራ የገባቸው የከተማው አስተዳዳሪዎች ተሰባስበው ከላይ በተሰጣቸው ትእዛዝ መሰረት አንድነትን የማጥቅያ ሌላ ሴራ ተጠቅመው መጥታችሁ የሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያውን ቅፅ ሙሉ በማለት ለተወካዮቻችን ጥሪ አደረጉ፡፡ የፓርቲው ተወካዮች ስራቸውን እየሰሩ ቅፁን የሚሞሉ እና የሚፈርሙ አባላትን በመመደብ ተወካይ ብቻ ወደ ወስተዳድሩ ፅ/ቤት ላኩ፡፡ የጠበቃቸው ግን የተቀናጀ ሴራ ነው፡፡ አንድነት ፓርቲን በህግ የሚያስጠይቅ እንዲሁም ያዘጋጁትን የሀይል ርምጃ ህጋዊ የሚያደርግ፤ ደብዳቤ ካስገባን 48 ሰዓታት ባነሰ ጊዜ ሰልፍ እወጣለሁ ብሎ ፓርቲው ነሓሴ 17/2005 ደብዳቤ እንዳስገባ ተደርጎ ይህንኑ ቀን የጠቀሰ ቅፅ አዘጋጅተው የአንድነትን ተወካዮች አንዲፈርሙ ተጠየቁ፡፡ ቀድሞውኑ ሴራው የገባው የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር በሰጠው መመርያ መሰረት ቅፁ ላይ የምንፈርመው ደብዳቤአችንን ያስገባንበትን ነሐሴ 13/2005 ቀን ከጠቀሰ ብቻ ነው በማለት የአንድነት ተወካዮች አንፈርምም አሉ፡፡

አንድነት ፓርቲን በጉልበትም በህግም ለማኮላሸት ኢህአድግ ያዘጋጀውን ሴራ በጥበብ ማክሸፍ ተቻለ፡፡ ኢህአዴግ ለሌላ ሴራ ማቀንቀኑን ወድያውኑ ተያያዘው፡፡

የፓርቲው ቀስቃሽ ቡድን በ50.000 የሚገመት በራሪ ወረቀት መበተኑን እና ከ5.000 በላይ ፖስተር በእለቱ በመለጠፍ የፓርቲውን መልእክት ለታፈነው የሮቤ ከተማ ህዝብ አደረሰ፡፡ በሁለት መኪና መጠነኛ ቅስቀሳ ካደረገ ከ 1፡00 ሰዓት በኋላ መኪናዎቹ ከነቀስቃሽ ቡድኑ ከነሀሴ 18/2005 እስከ እሁድ ነሀሴ 19/2005 ድረስ በታጣቂዎች ከቆሙበት አንዳይንቀሳቀሱ ታገቱ፡፡ የትራፊክ ፖሊሶችም መኪናዎቻችንን በማገት ያለቆቻቸውን ትዕዛዝ ተግባራዊ አደረጉ፡፡ በዚህ መሀል ነው በሽማግሌ ስም ያደራጃቸውን 15 የሚሆኑ የኦህዴድ ካድሬዎች ‹‹ነገ የሚከሰተው ደም መፋሰስ አሳስቦን ነው የመጣነው እናወያያችሁ›› በማለት ከምሽቱ 1፡30 ባረፍንበተ ሆቴል ተሰባስበው የመጡት፡፡ ለሀገር ሽማግሌ ክብር የሚሰጠው አንድነት ፓርቲ ሽማግሌዎች የተላኩበትን ዝርዝር መልእክት ካዳመጠ በኋላ የእሁዱን ሰላማዊ ሰልፍ በምንም ተአምር እንደማንሰርዘው፤ ይልቁንም የከተማው መስተዳድር ለፖሊስ የሀይል እርምጃ ውሰዱ ብሎ ያስተላለፈውን መመሪያ እንዲስብና ህገመንግስቱን እንዲያከብር ሽማግሌዎቹ ምክራቸውን ለገዢው ፓርቲ ባለ ስልጣኖች እንዲለግሱ መልእክት በመንገር ውይይቱ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ተጠናቀቀ፡፡ በኢህአድግ የተለመደ ቀመር የቅስቀሳ ጊዜያችንን በጉልበት እና በማስመሰል ለመስረቅ የተደረገውን የተለመደ ቅንብር አንድነት ፓርቲ ቀድሞ የሚያውቀው ጉዳይ በመሆኑ ሁለት ተደራዳሪዎችን ብቻ በመመደቡ ሌላው ግብረኃይል ሳይዘናጋ የቅስቀሳ ወረቀቱን በማሰራጨቱ ኢህአዴግ ያሰበውን አንድነትን የመነጠል ሴራ ሳይሳካለት ቀርቷል፡፡

እነዚያው የሀገር ሽማግሌዎች የተባሉ ግለሰቦች ‹‹መስተዳድሩ አሁን ሊያነጋግራችሁ ዝግጁ ነው፡፡ ቢሮ ድረስ ኑ እና ተወያዩ›› በማለት በሰላማዊ ሰልፉ ቀን እሁድ ከጥዋቱ 1፡00 ሰዓት እኛን ቀጥረውን በሰዓቱ ስንደርስ የኦሆዴድ ባለስልጣኖች ግን የጠዋቱ የቅስቀሳ ስዓታችንን ለመስረቅ ከጠዋቱ 1፡40 በሁለት ኮብራ መኪና እና ታርጋ በሌላት በአንድ መኪና በደህንነት ባለ ስልጣኖች ታጅበው መጡ፡፡

ውይይቱ በዞኑ ም/አስተዳዳሪ አቶ ሰሎሞን አወያይነት የከተማው ከንቲባ፣ የኦሆዴድ ተጠሪ የኮምኒኬሽን ሀላፊ ሌሎችም ከ15 ያላነሱ ባለ ስልጣኖች እንዲሁም በርካታ የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት ሦስት የመንግስት ካሜራዎች ተጠምደው ውይይቱ ተጀመረ፡፡

የሽማግሌ ካባ የለበሱት የኦሆዴድ ካድሬ የሆኑት የሀገር ሽማግሌዎች ተወካይ ነኝ ያሉት ግለሰብ ውይይቱን በንግግር ሲጀምሩ ‹‹እናንተ የነፍጠኛን ስርዓት ልታመጡብን ነው፡፡ እኛን ሳታነጋግሩ ሳንፈቅድላችሁ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንዴት አሰባችሁ? አሁንም ይህንን ሰላማዊ ሰልፍ አታደርጓትም፡፡ የሮቤ ህዝብ እኛን ዎክሎናል መንግስት እንኳን ቢፈቅድላችሁ እኛ ሽማግሌዎች አይደረግም ብለናል አቁሙ›› በማለት የተጫኑትን ዉሳኔ በሚደንቅ ሁኔታ አስተላለፉ፡፡ በእዚያው መድረክ የኢህአዴግ/ኦህዴድ ማንነት እና ጭንብል ለዓለም ህዝብ ተጋለጠ፡፡ አንድነት ፓርቲም ይህንን ከላይ እስከታች ባሉ ባለስልጣኖች የተቀነባበረውን ድራማ በካሜራ ቀርፆ ያስቀረ በመሆኑ በእጃችን የሚገኘውን የውይይቱን ይዘት የያዘውን ቨድዮ እንድትመለከቱ በአክብሮት  እየጋበዝን አንድነት ፓርቲ የኢህአዴግን እውነተኛ ገፅታ በመረጃ ማጋለጡን  አጠናክሮ ዛሬም ነገም ይቀጥላል፡፡

በሮቤ ከተማ ለቅስቀሳ የተላከው ቡድን በመስተዳድሩ ባለስልጣናት ትእዛዝ ከምሽቱ 4፡00 ስዓት አልጋ ከያዙበት ታይታኒክ ሆቴል በግፍ ተባረው፤ የያዙትን ቦርሳ እንኳን ከመኝታ ክፍላችው ሳያወጡ በግፍ አውላላ ሜዳ ላይ ወንጀል እንዲፈፀምባቻው የከተማው መስተዳድር የፍፀመውን መንግስታዊ ውንብድና ፓርቲአችን በዝምታ የሚያልፈው ጉዳይ አይደለም፡፡ የመኪና ሹፊሮቻችንን በውድቅት ሌሊት ጭንብል ባጠለቁ ከ 20 በላይ ታጣቂዎችን በማሰማራት በማስወረር በጉልበት ክፍላቸው ውስጥ በመግባት ስለተፈፀመው ወንጀል አንድነት ፓርቲ በህግ የሚጠይቅ ሲሆን ታላቁ የሮቤ ከተማ ነዋሪ ህዝብ መብቱን ለማስከበር ያደረገውን ትንቅንቅ አንድነት ፓርቲ ከልብ ያደንቃል፡፡ ምስጋናውንም በእዚህ አጋጣሚ ያቀርባል፡፡

ድል ለታፈነው የኢትዮጵያ ህዝብ!!!

   አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ

ነሐሴ 21 ቀን 2005 .

አዲስ አባባ

UDJ

 

 

የእኛ “መንግስት” –ከተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)

$
0
0

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ከተመስገን ደሳለኝ
“በእያንዳንዱም መንግስት የሚያድሩ ብዙ ልዩ ልዩ ነገዶች ይኖሩ ይሆናል፡፡ ስለ ሆነ መንግስት አንዱን ነገድ አጥቅቶ ሌላውን ነገድ ለመጥቀም ሥራው አይደለም፡፡ አስተካክለን ካሰብን ዘንድ መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡ ለአንዱ ነገድ ወይም ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት ለመንግስት የሚገባ ሥራው አይደለም”  ይህንን መግቢያ የወሰድኩት በልዑል የኢትዮጵያ መንግስት አልጋ ወራሽ ተፈሪመኮንን ማተሚያ ቤት የካቲት 1 ቀን 1917 ዓ.ም ከታተመው የነጋ ድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ‹‹መንግስትና የሕዝብ አስተዳደር›› መፅሀፍ ነው፤ ዛሬም ያለንበትን ዘመን ይዋጃልና፤ በተለይ ስለ‹‹ነገድ›› የተጠቀሰውን አርቀን ሰቅለን፣ ‹‹ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት›› የምትለዋን ሀረግ በወጉ ካጤንናት ለጊዜያችን በልክ የተሰፋች መሆኗን ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡
እናም የስርዓቱን የአስተዳደር ዘይቤ ያለፍርሃት አደባባይ ካዋልነው የቀድሞ ገዥዎቻችን የተጓዙበትን ጎዳና እየተከተለ መሆኑን ለመተንተን የምሁራንን ጥናት መጠበቅ ግድ አይለም፤ ምክንያቱም ለዓመታት የተመለከትነው እውነታ የሚነግረን የአመራሩን እና በዙሪያው የሠፈሩ የጥቅም ተጋሪ ግለሰቦችን ብልፅግና ታሳቢ ያደረገ፣ ከታግሎ መጣል ህግ የተቀዳ፣ የራስ ሀገርንና የራስ ሕዝብን በምርኮ ያስገበረ ፖለቲካ መንበሩን ነው፤ ገብር፣ ገብር፣ ገብር…!!
ዛሬ መንገድ ዳር ረሀብ አዙሮ የጣለው ወንድምህ ስቃይ እንደ ጥላ የሚከተልህ፤ ህፃናት በትምህርት ገበታቸው ላይ በጠኔ ተሸንፈው መመልከቱ የሰርክ አሳዛኝ ክስተት የሆነብህ ከሰው ሰራሽ ችጋር፣ ከሰው ሰራሽ የቀዬ ፍንቀላ፣ ከሰው ሰራሽ እርዛት… የመነጨ መርገምት እንጂ የሰማይ ቁጣ አይምሰልህ፤ እመነኝ መለስም ሆነ ተተኪዎቹ ስኬት አድርገው የሚሰብኩትም ይህንን ነው፤ ‹ሀገር አቀናን!› የሚሉትም ይህንን ነው፤ ሰሞኑን የሚያሰለቹህ ተረኛ ምሁራንም ‹‹ትምህርትና ጤናን በተመለከተ መለስ ‹እልል› የሚያስብል ሥራ ሰርቷል›› የሚሉህ ጣራና ግድግዳ እየቆጠሩ ነው፤ ይህ አይነቱ መደዴ ሙገሳም ለፕሮፓጋንዳ የሚሆን ሪፖርት ለማዘጋጀት ከሚረዳ ቁጥር የዘለለ አበርክቶ አንደማይኖረው አትዘንጋ፡፡
እውነት እውነት እልሀለሁ፡- ይህ የሆነበት ብቸኛው ምክንያት መንግስት በስልጣን ላይ ስለሚቆይበትመንገድ ብቻ መጨነቅን ግዴታው በማድረጉ ነው፤ ይህንን ለመረዳትም እያገባደድን ባለው ክረምት የመንግስት ትኩረት በምን ላይ አንደሆነ የሚያሳይ ማስረጃን ጨርፌ ላሳይህ፡፡
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- የእስልምና እምነት ተከታዮች መንግስት በሃይማኖታቸው ጣልቃ መግባቱን በመቃወም እና የታሰሩ ኮሚቴዎቻቸው እንዲፈቱ በመጠየቅ እያደረጉ ያለውን ትግል በሰላማዊ መንገድ አጠንክረው ሲቀጥሉ፤በተቃራኒው ‹‹ፀጥታ አስከባሪዎች›› አንዳንዴ በጥይት፣ አንዳንዴ በአስለቃሽ ጢስ፣ አንዳንዴ በማጋዝ…ምላሽ ሲሰጡ…
በርግጥ መንግስት ከኃይል እርምጃው በተጨማሪ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎችን (በምን አግባብቶ ወይም በምን አስፈራርቶ እንደሆነ ባይታወቅም) ወደ አደባባይ በማስወጣት መብት ጠያቂዎቹን ከ‹‹አክራሪ››ነት እና ‹‹ወሃቢዝም››ነት ጋር አያይዘው የውግዘት በረዶ እንዲያዘንቡባቸው እያደረገ ነው፡፡ ኢቲቪም ይህንን ኩነት እየተከታተለ ማራገቡን ቀጥሎበታል፤ ‹‹የቲፒ ከተማ ነዋሪዎች ‹አክራሪዎችን አወገዙ››፤ ‹‹በደቡብ ወሎ ኩታ በር ዞን አንድነት ፓርቲ ህገ-ወጥ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰልፍ ተካሄደ››፤ ‹‹የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ‹የሼሁ ግድያ ድራማ አይደለም› አሉ፣ ‹የሼህ ኑሩ ኢልም ነው፣ የአሸባሪዎች ብር ነውም›ብለዋል››፤‹‹የመርሀቤቴ ነዋሪዎች ፅንፈኞችን በመቃወም የአቋም መግለጫ አወጡ››፤…
ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- አንድነት ፓርቲ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የ‹‹ፀረ-ሽብር ሕጉ›› እንዲሰረዝና የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ እና የአዳራሽ ስብሰባዎችን እያካሄደ ነው፤ መንግስትም አንዳንዴ የአፀፋ የድጋፍ ሰልፍ ሲያካሄድ፤አንዳንዴ የአዳራሽ ስብሰባዎች ከመካሄዳቸው አስቀድሞ ‹መጋኛ› ሲሆንባቸው፤ አንዳንዴም የአስተባባሪዎቹን መኪና ጎማ ሲያፈነዳ፤ አንዳንዴም አዳራሽ ከልክሎ ሲያደናቅፋቸው… መዋሉ ፋታ የነሳው ይመስላል፤ በወላይታ የተጠራውን የአዳራሽ ስብሰባም ‹በጠቅላይ ሚኒስትሩ የትውልድ ቦታ እንዴት ተደርጎ!›› ያሉ ካድሬዎች የአንድነት ሰዎችን አዋክበው ስብሰባውን አክሽፈዋል፤
ክረምቱእንዲህእየተገባደደነው፡-ገዥው ፓርቲ ‹የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ አንደኛ ሙት ዓመት አከብራለሁ› በሚል መላ ኢትዮጵያን ችግኝ መትከያ፣ መላ ዜጎቿን ደግሞ ወደ አርሶ አደርነት በአስማት የቀየራቸው አስመስሏቸዋል፤ቴሊቪዥንና ራዲዮንም አስፈላጊነታቸው በየመንደሩ ችግኝ መተከሉን እየተከታተሉ መዘገብ ብቻ እስኪመስል ድረስ እንዲህ ሲሉ ጀምበር ወጥታ ትጠልቃለች፡- ‹‹የላይ አርማጮህ ነዋሪዎች ችግኝ ተከሉ››፣ ‹‹በመቀሌ ከተማ ‹ዘመቻ መለስ› በሚል የችግኝ ተከላ ተካሄደ››፣ ‹‹አቃቂ ኮረብታ ላይ በሚሊዮን የሚቆጠር ችግኝ በኦሮሚያ ፌደራል ፖሊስ አባላት ተተከለ፤ ቦታውም ‹መለስዜናዊ ኮረብታ› ተብሎ ተሰይሟል››፣ ‹‹በምዕራብ ሀረርጌ አስራ ሰባት ሚሊዮን፣ በወልበራ አስራ አራት ሚሊዮን ችግኝተ ተክሏል››፣ ‹‹በመንዝ ላሎ ወረዳ ተቆጥሮ የማያልቅ ችግኝ ተከላ ተደርጓል››፣ ‹‹የብአዴን አመራርና ካድሬ በባህር ዳር ከተማ በቢሊዮን የሚቆጠር ችግኝ ተከሉ፤ በፕሮግራሙ ላይ ጓድ አዲሱ ለገሰ ‹ችግኝ የምንተክለው አገሪቱ በአረንጓዴው ልማት በአለማችን ማግኘት የሚገባትን ቦታ እንድታገኝ ለማድረግ ነው› ሲል፣  ጓድ በረከት ስምዖን ደግሞ ‹ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በአለማችን በአንድ ጊዜ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ችግኝ እየተከሉ ያሉባት ብቸኛ ሀገር ናት› ብሏል››፤‹‹ዝክረ መለስ 1ኛ ዓመት መታሰቢያን ምክንያት በማድረግ ከሐምሌ አስራ አምስት ቀን ጀምሮ ሁሉም ቀበሌዎች በስሙ ‹ፓርክ› ሰይመው ችግኝ ተከላ እያካሄዱ›› መሆኑን ደግሞ የባህር ዳር ከተማ ከንቲባ መግለፁን የአማራ ክልል ብዙሃን መገናኛ ዘግቧል፤ ‹‹በወልቂጤ ከተማ በተደረገው ችግኝ ተከላ ላይም አንዲት ወጣት ‹መለስ ለሴቶች የተለየ አመለካከት ነበረው›› ማለቷም በዘገባው ተጠቅሷል፤ …ማን ነበር የመለስ ራዕይ ‹ችግኝ መትከል ነው› ያለው? …ኢህአዴግ ይሆን?
ከዚሁ ጎን ለጎን (አሁንም ሙት ዓመቱን ለማሰብ) በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የእግር ጉዞ ተደርጓል፣ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓትም ተካሄዷል፤መነሻውን መቀሌ፣ መድረሻውን አዲስ አበባ ያደረገ ‹‹የመለስ ቱር አረንጓዴ ልማት›› የብስክሌት ውድድርም ሊጠናቀቅ ገና አንድ ሳምንት ይቀረዋል፤ በብሄራዊና ሀይማኖታዊ በዓላት ቀንለሃያ አንድ ጊዜ ይሰማ የነበረው የመድፍ ድምፅም፣ የመለስን አንደኛ ሙት ዓመት ለማብሰር ተተኩሷል፤ …በግድ አልቅሱ፣ በግድ ተዝካር አውጡ፣ በግድ ችግኝ ትከሉ፣ በግድ ተወያዩ፣ በግድ አደባባይ ውጡ፣ በግድ የፎቶ ግራፍ ኤግዚቢሽን ጎብኙ፣ በግድ..  ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ እና የትምህርት ሚኒስትሩ ሽፈራው ሽጉጤ ከአንድ ሺህ ሰባት መቶ በላይ ለሚሆኑ የዩኒቨርስቲ ከፍተኛ መምህራን ‹የአቅም ግንባታ ስልጠና› እየሰጡ ነው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምሁራኖቹን ማሰልጠን ያስፈለገበት ምክንያት ‹‹ብቃት ያለው ምርጥ የተማረ ኃይል ለማፍራት››መሆኑን ቢነግርህ አይግረምህ፤ ይህ ኢትዮጵያ ነውና የዐዋቂነት ማረጋገጫው መማር፣ ማንበብ፣ መመራመር… አይደለም፣ የፖለቲካውን ኃይል መያዝ እንጂ፤ ‹ስልጣን ላለው ሁሉምሚስጥረ-ጥበብይገለፅለታል› እንዲል አብዮታዊ ዲሞክራሲ መለስ ዜናዊም በሁሉም መስክ ‹አስተማሪ› ነበር፤ የህግ ባለሙያዎችን ሰብስቦ የሀገሪቱን ወንጀለኛ መቅጫ ህግ ትርጓሜ ሲተነትን ደጋግመህ ሰምተኸዋል፤ በቀጣዩ ቀን ደግሞ ለግብርና ባለሙያዎች ከውሃ ማቆር እስከ በላብራቶሪ የሚዳቀል ምርጥ ዘር ድረስ ባሉጉዳዮችዙሪያ የሁለት ቀን ማብራሪያ መስጠቱን ታስታውሳለህ፤ እመነኝ ተተኪው ጠቅላይ ሚኒስትርም ይህንኑ ነው እያደረገ ያለው፤  የሆነ ሆኖ ኃ/ማርያም ለምሁራኖች ከሙያቸው ጋር ስለተያያዙ ጉዳዮች ጭምር በሰጣቸው ስልጠና ላይ እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀርቦለት ነበር ‹‹የኢንዱስትሪዎች በበቂ ሁኔታ አለመኖሩ፣ በክፍል ውስጥ የምናስተምረውን ንድፈ ሃሳብ በተግባር ለማሳየት እንቅፋት ሆኖብናል››፤ በርግጥጠቅላይ ሚንስትሩ‹‹መፍትሄ››ያለውን የተናገረው ብዙም ሳይጨነቅ ‹‹እኔ ኢንዱስትሪን ‹ዲፋይን› የማደርገው ግብርናም ኢንዱስትሪ ነው ብዬ ነው››በማለት ነበር፤…ግና!ይህ እንዴት ሊሆን እንደሚችል በተጨባጭ አላብራራም፡፡ለምሳሌ ህክምና የሚያጠና ተማሪ በምን መልኩ በሞፈርና ቀንበር የተግባር ልምምድ ማድረግ እንደሚችል፤ወይም ፖለቲካ ሳይንስ የሚያጠና ተማሪ የተግባር ልምምዱን በግብርና ኢንዱስትሪ እንዴት ሊወጣው እንደሚችል? ማለቴ ነው፡፡
ለዓመታት በርካታ ምሁራን ብቃት አልባ ተማሪዎች እንደ ሰማይ ከዋክብት የመብዛታቸው መንስኤን ከትምህርት ፖለሲው ጋር የሚያነፃፅሩበትን ሀቲት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ ባገኘው የሀገር መሪነት ስልጣን ገልብጦ በዩንቨርስቲ ቆይታው መምህራኖቹ የነበሩትንም ጭምር ‹‹አቅም አንሷችኋልና-እገነባችኋለሁ›› ሲል ከመስማት የከፋ እንደ ሀገር ክሽፈት የለም (በነገራችን ላይ ከወራት በፊት ለኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በረከት ስምዖን፣ ቴውድሮስ አዳህኖም፣ ሶፍያን አህመድ በአጠቃላይ ሁሉም የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት አንድ ህንዳዊ ፕሮፌሰር በኢህአዴግ ጽ/ቤት ‹‹ልማታዊ መንግስት›› እንዴት ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል ሲተነትንላቸው፣ እነርሱም ደብተርና እስክርቢቶ ይዘው በንቃት ሲከታተሉ የቴሌቪዥ ዋና ዜና ሆኖ የቀረበበትን ምክንያት ዛሬም ድረስ ሊገለፅልኝ አልቻለም፤ በተለይም ፕሮፈሰር እንድርያስ እሸቴ ‹‹በቃሉ የፀና…›› በሚል ርዕስ መለስን አስመልክቶ በተዘጋጀ ዶክመንተሪ ፊልም ላይ ‹‹በዓለማችን ለመጀመሪያ ጊዜ ልማታዊ ስርዓተ መንግስት ‹ዴሞክራሲያዊ ሊሆን ይችላል፤ መሆንም አለበት› ብሎ በአደባባይ የተከራከረው እኔ እስከማውቀው ድረስ መለስ ነበር›› ማለቱን፣ ተተኪዎቹ ፍልስፍናውን ገና እየተማሩት ከመሆኑ አንፃር ስናየውሀገራችን ያለችበት ሁኔታ ጉዞው ወዴት ነው? ያስብላል፡፡ …ከቶስ በተማሪ ፖለቲከኛ የሚተዳደር ሕዝብ ከኢትዮጵያ በቀር ወዴት ይኖራል?)

ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- የህዳሴውን ግድብ ከዳር ለማድረስ በቂ ገንዘብ ስላልተገኘ ተደጋጋሚ የቦንድ ሽያጭ እየተካሄደ ነው፤ አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞችም በካድሬ ባልደረቦቻቸው ጫና በድጋሚ ቦንድ ለመግዛት መወሰናቸው ተሰምቷል፤ በርግጥ ከፍተኛ የኢህአዴግ የአመራር አባላት በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ቦንድ እንዲገዙ ለመቀስቀስ የአዘጋጇቸው ስብሰባዎች ‹‹ቅድሚያ የዜጎች መብት ይከበር›› ባሉ የሀገራችን ልጆች መክሸፉም የክረምቱ የመንግስት ዋና ሥራ ነው፤ ክረምቱ እንዲህ እየተገባደደ ነው፡- በነቢብ የኢትዮጵያ፣ በገቢር የገዥው ፓርቲ የግል ንብረት የሆነው ቴሌቪዥን ጣቢያ ባለፉት ሶስት ወር ብቻ ከሃያ በላይ ‹‹ዶክመንተሪ ፊልም›› አሳይቷል (ገና ይቀጥላልም) በርዕሳቸው እንደሚከተለው እንዘርዝራቸው፡- ‹‹ኢፍቲን›› በሶማሊያ ላይ የሚያጠነጥን፣ ‹‹የጥቁር ህዝቦች ልሳን (መለስ በአፍሪካ)››፣ ‹‹ከፓን አፍሪካ እስከ አፍሪካ ህዳሴ›› የጠቅላይ ሚንስትር መለስን ህይወት የሚዳስስ፣ ‹‹ዘመነ አፍሪካ››፣ ‹‹የአፍሪካ ልሳን-መለስ››፣ ‹‹መለስ ማን ነው?››፣ ‹‹ሀገሬ-ቤቴ››፣ ‹‹ባለራዕዮቹ›› ስራ ፈጠራ ላይ የሚያተኩር፣ ‹‹ደውል›› እና ‹‹ደውል 2›› ህገወጥ-የሰዎች ዝውውርን በተመለከተ (በተለያያ ጊዜ የተላለፉ)፣ ‹‹የዲያስፖራ የልማት እንቅስቃሴ››፣ የካርታ ስራ ድርጅትን በተመለከተ፣ ‹‹የጥልቅ አስተሳሰብ ባለቤት›› በፕ/ር እንድርያስ እሸቴ ህይወት ዙሪያ የሚያጠነጥን፣ ምድር ባቡር ኮርፕሬሽንን በተመለከተ፣ ‹‹ያልተለመደ ጉብኝት›› የአዲስ አበባ አስተዳደር የአምስት ዓመት የመንግስት ግንባታዎችን በተመለከተ፣ ‹‹ሼህ ኑር ለምን ሞቱ?›› የደሴውን ሼህ ኑር ይማምን ግድያ በተመለከተ፣ ‹‹የተስፋ ስንቅ››፣‹‹በቃሉ የፀና›› በድህረ መለስ ላይ የሚያተኩር፣ ‹‹ያልተጠኑ ገፆች›› በመለስ ዜናዊ ህይወት ዙሪያ (በርግጥ በዚህ ፊልም እህቱ ጠላ፣ ወንድሙ አንባሻ በመሸጥ መተዳደራቸውን በምስልም በድምፅም ማቅረቡ ምን የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ እንደሆነ ለማወቅ ግራ ያጋባል፤ …ምናልባት እንዲያ እየዘረፈ ለቤተሰቦቹ ‹ሶልዲን› የማይሰጥ ‹ቆነቋና› ነበር ለማለት ይሆን? ወይስ ለአዜብ መስፍን ‹የወር ቀለባችንን እንቸገራለን› የአንድ ሰሞን ማስተዛዘኛ ምስክር ፍለጋ ነው?

በጥቅሉ ለኢህአዴግ ሕዝብን የማስተዳደር፣ ሀገርን የመምራት መገለጫ ይህ ነው፤ ሌላ አይደለም፤ ግና! ለዘመናት ያልተመለሱ ጥያቄዎቻችን ዛሬም መጮኻቸውን አላቋረጡምና እነሆ እንዲህ ቀጥለዋል፡- ሀገር ማስተዳደር ‹መለስ ጀግና ነበር› እያሉ ማሰልቸት ነውን? የመንግስትስ ስራ (ግዴታ) ምንድር ነው? ሀገሪቱን ‹‹መለስ-ፓርክ›› ወደሚል ስያሜ ከመቀየራችሁ በፊት፣ ለጤፍ ዋጋ አለቅጥ መናር ምክንያቱን ስለምን መመርመር ተሳናቸው? ሀገሪቱን በ‹አራጣ› እንደያዘ ስግብግብ ነጋዴ በሚሊዮኖች ህይወት ላይ የማይሞላ ‹ሳፋ› ደቅኖ አዋጣ፣ ግዛ፣ ክፈል፣ ገብር… እያለ የሚያስጨንቀው ማን ነው? ስለመለስ ‹የሃሳብ ምጡቅነት› መስካሪ ምሁራኖቻችን ለጎዳና ኑሮ የተዳረጉ ኢትዮጵያውያን ስንት ሚሊዮን እንደደረሱ እና እልፍ አላፍት ታዳጊዎቻችን በሴተኛ አዳሪነት እንደተሰማሩ የምትነግሩን መቼ ነው?እንዲህ የመሆኑ ምክንያትስ በማን ይሆን? ‹የሁለት ዲጂቱ›ዕድገት ሸክምን የማለዘብ አቅም ከሌለውፋይዳው ምንድር ነው? ‹ሳቅ ትዝታ› ስለሆነባቸው ጎጆዎች ለምን አትነግሩንም? መለስ ‹ያለመለማት› ኢትዮጵያ ወዴት ትሆን? ‹ፖለቲካ› ማለትስ ይህ ነውን? …ነጋ ድራስ ገ/ህይወት እንዳሉት ‹‹…መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡›› የመተራረሚያው ጊዜም በጣም ያለፈ ይመስለኛል፡፡ አገዛዙን ‹እንደ መንግስት› መቀበሉም እንዲሁ፡፡

ህዝበ-ሙስሊሙን ያለአግባብ በስጋት መፈረጅ፤ ማዋከብና መግደል በአፋጣኝ ይቁም!!

$
0
0

የነፃነት ጐህ

muslim1የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት አንቀጽ 11 ቁጥር 3 ”መንግስት በሀይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፤ ሀይማኖትም በመንግስት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም ” ይላል፡፡በሀገራችን ከንጉሱ ዘመን ጀምሮ በወታደራዊው ደርግ እንዲሁም አሁን ስልጣን ላይ ባለው ወያኔን ጨምሮ ሁሉም ሀይማኖቶች ከመንግስት ጣልቃገብነት ነፃ ሆነው አያውቁም። ፍትህ፣ ነጻነት፣ እኩልነት እና አንድነት ለብዙ ሀይማኖቶች መሰረታዊ እሴቶች ናቸው፡፡ እነዚህ እሴቶች ላለፉት 22 ዓመታት በዘረኛው የወያኔ መንግስት እየተሸረሸሩ እና እየተመናመኑ ዛሬ ከነአካቴውም ለመጥፋት ተቃርበዋል፡፡ ስለመሰረታዊ የሰው ልጅ መብት እና ነጻነት እንዳይወራ የወያኔ የጥይት አፈሙዞች በእያንዳንዱ ሰው እና የህዝብ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ተደቅኗል፡፡የእምነት ቦታዎችንም ሳይቀር በመድፈር ህዝበ-ምዕመኑ የኔ የራሴ የሚለው የአምልኮ ቦታ እና የአምልኮ ስርዓት እንዳይኖረው እያደረገ ነው።

ወያኔ አምባገነናዊ ስርአቱን ለማስቀጠል ሲል የዕምነት ተቋማትንና መሪዎቹን በቁጥጥሩ ስር ሲያደረግ ኖሯል፡፡ ይህ አንባገነናዊ ድርጊት በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይም ተግባራዊ በመደረጉ ምዕመናኑ የመንግስትን ድርጊት በመቃወም ላለፉት ሁለት ዓመታት ጠንካራ ሰላማዊ ትግል አድርገዋል፤ እያደረጉም ይገኛሉ፡፡ መንግስት አለመግባባቱን ለመፍታት የቀረቡለትን ሶስት ጥያቄዎች ከመፍታት ይልቅ በማን አለብኝነት የትግሉን ግንባር ቀደም መሪዎች ከማሰር ባለፈ በምዕመናኑ ላይ ኢሰብአዊ ጥቃቶችን ማድረሱ የአደባባይ ሃቅ ነው፡፡  ለወያኔ ህገመንግስትን የመጣስ ድርጊት አዲስ ባህሪው ባይሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ እያደረሰ ያለው የመብት ረገጣውን ማጠናከሩ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ደርሷል፡፡ ይህ የመንግስት ሀይሎች ድርጊት ችግሩን ከማባባስ ባለፈ የሚያመጣው መፍትሄት አይኖርም፡፡

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ላነሷቸው ግልፅ የመብት ጥያቄዎች ብልሀት የተሞላበት ምላሽ መስጠት ያቃተው ወያኔ እየወሰዳቸው ያሉት ኢህገመንግስታዊ እርምጃዎች፤ በሙስሊሙ ሕብረተሰባ ላይ እየደረሰ ያለው የሰብአዊ መብት ጥሰት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ከመንግስት ሌላ ተጠያቂ የሚደረግ አካል አይኖርም፡፡ ስለሆነም ይህ አይነቱ ህገወጥና ሀላፊነት የጎደለው ድርጊት እንዳይቀጥል ማድረግ ከተጠያቂነት ያድናል፡፡ መንግስት የተበደሉ ዜጎችን ቅሬታ በማጣራትም በህገወጥ ድርጊት በፈፀሙ ሃይሎቹ ላይ በአፋጣኝ እርምጃ መውሰድ አለበት፡፡

 

ሃይማኖታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ችግሮች ሲከሰቱ ሃይማኖታዊ ወይም መንፈሳዊ የሆኑ መፍትሔ ማፈላለግ ብቸኛው አማራጭ ነው፡፡ በእምነት ተቋማት ውስጥ ለሚነሱ ጥያቄዎች ፖለቲካዊ መልስ መፈለግ ችግሩን ከማስፋፋትና ወደ አላስፈላጊ ውዝግቦች ከመክተት ውጪ የሚፈጥረው በጎ ለውጥ አይኖርም፡ ፡ የቤተ-ክርስቲያን አለመግባባቶችን ቤተ-መንግስት ለማስታረቅ ሲሞክር ምን ይፈጠር እንደነበር ታሪክ ደጋግሞ አሳይቶናል። በቅርቡ እንኳ በዋልዳባ ገዳምና በምእመናኑ ላይ የተቃጣው ሰይጣናዊ፤ በትዕቢትና በማናለብኝነት የእምነትን ቀይ መስመርን በመጣስ የተወሰደ ጥቃት ሁለቱንም የወያኔ ቁንጮዎች መለስ ዜናዊንና አባ ፓውሎስን ግብአተ መሬት ማፋጠኑ ይታወሳል። መንግስታዊ ጣልቃ ገብነቶች ከእለት ወደ እለት እየገዘፉና እየጠነከሩ ሲመጡ የችግሮች ስር መስደድም የዚያኑ ያህል እየከፋ ይመጣሉ፡፡ ስለዚህ በእስልምና እምነት ላይ እየተደረገ ያለው መንግስታዊ ጣልቃ ገብነት በሀገሪቱ ህገ-መንግስት ላይ የተገለፀውን መንግስትና ሀይማኖት መለያየታቸውን የሚጥስ በመሆኑ አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃ ይወሰድ ዘንድ ግድ ነው፡፡ ይህ ካልሆነ ግን በክርስትና እምነት እንደተደረገው ሁሉ፤ የህዝበ ሙስሊሙ ፀሎትና ልመና ጣልቃ ገብተው እየበጠበጡ ያሉ አምባገነኖች ላይ መቅሰፍት እንደሚያወርድ ጥርጥር የለውም።

በአወሊያ መጅሊሱ እንዲወርድ ሲባል የተጀመረው ሰላማዊ አቀራረብ አሁን ከአዲስ አበባም አልፎ ወደሌሎች ክፍለ ሀገራት  ደርሶ መሳሪያ አማዟል፡ ፡ ለዚህም ማሳያ በቅርቡ በመዲናችን አዲስ አበባ፤ ደሴና ኮፈሌ ላይ የመንግስት ሃይሎች በንፁሃን የሙስሊም ወገኖች ላይ ያደረሱት መጠነ ሰፊ ጥቃትና ግድያ መጥቀስ ይቻላል። በዚህም ሊያበቃ እንደማይችልም ሁኔታዎችን ተመልክቶ መገመት ይቻላል፡፡ ፖለቲካዊ ማንነት ባላቸው ግለሰቦችና ካድሬዎች ቤተ-እምነቶችን መምራት የኋላ ኋላ ይዞ የሚመጣው መዘዝ ሀገራዊ ቀውስ ነው፡፡ ለተቃውሞ የወጣውን ህዝበ ሙስሊም ሰለፊያ በሚል ቅፅል መጠሪያ ስም በመስጠት ዓላማቸውንም ከሽብር ጋር በማያያዝ መፈረጅ ሁኔታውን ከማባባስ ውጪ ዘላቂ መፍትሄ ሊያመጣ አይችልም፡፡

ሕጋዊ መብትን በግልም ሆነ በኅብረት መጠየቅ ሽብርተኛ አያደርግም፤ ሽብርተኛ የሚያደርገው መብታቸውን የሚጠይቁትን መግደል፣ መደብደብና ማሰር ነው፤ ዓለማዊውን ሥርዓት የማይነካውን፣ ከአምላኬ ጋር ግንኙነት ለመፍጠር የመረጥሁትን መንገድ አክብሩልኝ፤ በሌላ መንገድ ወደአምላኬ እንድሄድ አታስገድዱኝ ማለት ሽብርተኛነት አይደለም፤ ሽብርተኛነት የሚሆነው በሰዎች ላይ ባዕድ የሚሉትን እምነት መጫን ነው፤ ሽብርተኛነት የሚሆነው አትጫኑብኝ እያለ በሰላማዊ መንገድ የሚጮኸውን ሰው መደብደብ፣ ማሰርና መግደል ነው፤ ሽብርተኛነት የሚሆነው የሰዎችን ቅዱስ ቦታ በጥይትና በደም ማርከስ ነው፤ ሽብርተኛነት የሚገለጠው ሰላሜን ጠብቁልኝ እያለ በሚጮኸው ሰው ሳይሆን በጉልበቱ ብቻ ተማምኖ ሰላምን በሚያደፈርሰው ነው፤ ሕዝብ ሰላምን ሲያገኝ ይሠራል፤ ያመርታል፤ ኑሮውን ያሻሽላል፤ ይዝናናል፤ ይህ ሁሉ ጥጋብን ያመጣል፤ ሲጠግብ የሚያስቸግረውን እንዳይጠግብ መበጥበጥ የሚፈልጉ አይጠፉም፡፡ ጮሌነት ዕድሜ አለው፤ የጮሌነት ዕድሜ በጣም አጭር ነው፤ ነገር ግን ጠንቁ ከነኮተቱ በልጅ ላይ ያርፋል፤ የጮሌው ኃጢአት ልጁን አዋርዶ ያቃጥላል፤ ማንም ለማንም የሚመኘው መንገድ አይደለም፡፡

 

ስለዚህ ሙስሊም ወገኖቻችን ጥያቄያቸውን ህገ-መንግስቱ በፈቀደላቸው በሰላማዊ እና ህጋዊ መንገድ እስካቀረቡ ድረስ መንግስት አግባብነት ያለውን መፍትሄ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ የሃይማኖቶች ነፃነትን በዚህ አካሄድ እየጨፈለቁ መሄድ ትርፉ ስርዓታዊ ኪሳራ ብቻ ነው፡፡ የሃይማኖቱ ተከታዮች ይወክሉናል ብለው የመረጧቸውን የአመራር አባላትንም ሆነ ምዕመኑን ማሰር፤ ማንገላታትና መግደል በሀገሪቱ ውስጥ ህገ- መንግስታዊነት እና የህግ የበላይነት ያለመኖሩ ማሳያ ነውና ይኼ አምባገነናዊ እርምጃ በአስቸኳይ መቆም አለበት።

 

ድል ለጭቁኑ ህዝበ ሙስሊም!!

 

ፀሃፊውን በኢሜል yentsanetgohe@gmail.com ያገኙታል።

የጋዜጠኝነት ሙያና ፤ በውጪ ያሉ ሚዲያዎች አገልግሎት ሲገመገም

$
0
0

ከደምስ በለጠ

Signature --- Image by © Royalty-Free/Corbisስለጋዜጠኝነት ስናስብ የመጀመሪያው ጥያቄ የሚሆነው ጋዜጠኝነት “journalism” ፤ ምንድነው ? ጋዜጠኝነት መቼ ተጀመረ ? እንዴትስ አደገ ? የጥሩ ጋዜጠኛ መገለጫ ባህሪዎችስ ምንድን ናቸው? የሚለው ይሆናል :: ጋዜጠኝነት የተፈፀሙ ፤ የተደረጉ ሁኔታዎችን ፤ በጋዜጣ ስርጭት ፤ በመፅሄት ፤ በመፅሃፍ ፤ በራዲዮ ፤ በቴሌቪዥን ፤ አሁን ደግሞ …..ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

 


የነጻነት ዋጋ ስንት ነው? –በአቤል አለማየሁ

$
0
0
በአቤል አለማየሁ
20130821_151318

 

በልጅነቱ ከቤተሰቡ ተደብቆ ጀብሎ ሆኖ ሰርቷል፤ ሲጋራ እና ማስቲካ ሻጭ ማለት ነው፡፡ በሰፈሩ የታወቀ የብይ ተጨዋችም ነበር፡፡ ‹‹አሁንም እንደ ከረንቦላ ቆሞ መጫወት ቢቻል ብይ ብጫወት ደስ ይለኛል ነበር›› ባይ ነው፡፡ ዛሬም ድረስ የልብስ ስፌት መኪና ‹‹ሾፌር›› የሆኑት አባቱ ሰይፉ ማሩ ጉንጆ አጠገብ ቁጭ ብሎ እየተከፈለው ልብስ ይዘመዝም ነበር፡፡ [አቶ ሰይፉ ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ታምራት ላይኔ እና ከዶ/ር ብርሃኑ ጋር በአንድ ቡድን ውስጥ አብረው ኳስ ተጫውተዋል፡፡] ጨዋታ አዋቂ እና ታታሪዋ እናቱ አይናለም ሲማ የእሱም ሆነ የቤተሰቡ ተምሳሌት የሆኑ ዛሬ እሱ ለደረሰበት ደረጃ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ጠንካራ ሴት ናቸው፡፡ መፍጠር ይሻ የነበረውን የቢዝነስ ኢምፓየር የመንግሥት ፖሊሲዎች እና የአፈጻፀም ችግሮች ተግዳሮት ሲሆኑበት ፖለቲከኛ በመሆን ለመታገል በፓርቲ ፖለቲካ ስር ተጠቃለለ፤ የቅንጅት ውህድ አንድ አካል በነበረው ኢዴሊ፡፡ ከምርጫ 97 በኋላ በተፈጠረው ጦስ ቃሊቲ የተላኩት አመራሮች ከእስር ከተፈቱ በኋላ በተፈጠረው አንድነት ፓርቲ ውስጥ የፖለቲካ ትከሻው እየጎላ መጣ፡፡ ይህ ሰው በምርጫ 2002 ብቸኛው የመድረክ ዕጩ በመሆን ፓርላማ የሚገኘው አማራጭ ድምጽ አቶ ግርማ ሰይፉ ነው፡፡
ከጥላቻ ፖለቲካ የነጻው ግርማ ዛሬ (ሐምሌ 3/2005 ዓ.ም) ልደቱ ነው፤ 47 ዓመቱን ጭጭ ያደረገበት፡፡ ታዲያ ዛሬ ልደቱን የሚያከብረው ኬክ ቆርሶ ሳይሆን ‹‹የነጻነት ዋጋ ስንት ነው?›› የሚል ባለ 235 ገጽ መጽሐፉን በ10፡30 – 22 ማዞሪያ አካባቢ በሚገኘው በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አዳራሽ በማስመረቅ ነው፡፡ በአምስት ክፍል፣ በ19 ምዕራፍ የተከፈለው ይህ መጽሐፍ ስለ ፖለቲካ አጀማመሩ፣ በኢዴሊ፣ በቅንጅትና በአንድት ስላሳለፈው የፖለቲካ ጉዞው የተመለከታቸውን መጻፍ አለባቸው ያላቸውን ጉዳዮች የዳሰሰበት ሲሆን እንዴት የምርጫ 2002 ክስተት እንደሆነም በስፋት የሚነግረን አለው፡፡ የግል ታሪኩም ተካቶበታል፡፡ [የግል ታሪኩን ለመሰብሰብ አብሬው በእናት እና አባቱ ቤት ተገኝቼ ከላይ የጠቀስኳቸውንም ሆነ ሌሎች አስገራሚ ሁኔታዎችን ማዳመጥ ችያለሁ፡፡] እንደነገረኝ ከሆነ ከሆነ አነጋጋሪ ሊሆኑ የሚችሉ፣ በድፍረት የተጻፉ ፖለቲካዊ ጉዳዮችን መጽሐፉ ይዟል፡፡ ዋጋው 50.70 ብር ነው፡፡ ከነገ ጀምሮ ገበያ ላይ ይውላል፡፡ የምርቃቱ አካል ትሆኑ ዘንድ በአዳራሹ እንድትገኙ ግርማ ጋብዟችኋል፡፡ ፖለቲከኞቻችን መጽሐፍ እየጻፉ መሆናቸው በራሱ መልካም ነገር ነውና እናበረታታ፡፡
የሚገርመው በቅርቡ በለቀቅነው ‹‹ኢትዮጵያን ማን ይታደጋት?›› በሚለው መጽሐፋችን ላይ የውይይቱ አካል ካደረግናቸው ውስጥ በቀጣይ ጊዜያት ብዙዎቹን እንደ ግርማ ሁሉ በመጽሐፍ ታገኟቸዋላችሁ፡፡ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ መጽሐፍ ጀምረዋል፡፡ የሌ/ኮሎኔል ደበላ ዲንሳ ቤተሰቦች ደበላ ጀምረውት ሳይጨርሱት የሄዱትን መጽሐፍ ለማጠናቀቅ ተፍ ተፍ እያሉ ነው፡፡ የፕሮፍ ብዕር እንደምታውቁት አይሰንፍም፡፡ ሙሼ ሰሙ በቀጣዩ ዓመት አነጋጋሪ መጽሐፍ ይዞ እንደሚመጣ ነግሮኛል፡፡ አምባሳደር ጥሩነህ ዜና የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የአንድ ሲዝን የሥራ ዘመናቸው እንዳበቃ የመጀመሪያ ተግባራቸው መጽሐፍ መጻፍ ነው፡፡ ዶ/ር ወሮታው ሁሌም ለአዲስ ሥራ በተጠንቀቅ የቆሙ ሰው ናቸው፡፡ ሁለቱም የሃይማኖት ልሂቃን እየጻፉ ነው፡፡ አሁን ላይ ያለውን ሀሳባቸውን ባላውቅም ተመስገን ሁለተኛውን፣ ዳዊት የመጀመሪያውን መጽሐፋውን ጨረሱ ከተባለ ቆይቷል፡፡ ለሁሉም መልካሙን ተመኝቻለሁ፡፡

የሕወሐት ባለስልጣናት የአሜሪካ ቆይታ፤ የከዱ አሉ – (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

$
0
0

ከኢየሩሳሌም አርአያ

abay welduበአባይ ወልዱ የሚመራውና ሰባት ከፍተኛ የሕወሐት ባለስልጣናት የተካተቱበት ቡድን በአሜሪካ አራት ከተሞች ባካሄደው ስብሰባ በተለይ በላስቬጋስ ጠንካራ ተቃውሞ እንደገጠመው በስፍራው የተገኙ ምንጮች አስታወቁ። ቡድኑ በዋሽንግተን ኢትዮጲያ ኤምባሲ በጀመረውና በመቀጠል በላስቬጋስ፣ ሲያትልና ካሊፎርኒያ ከተሞች ባካሄደው ስብሰባ “አላማ” አድርጎ የያዛቸው ጉዳዮች እንደነበሩ የጠቆሙት ምንጮች፣ እነሱም፥ “የመለስ ፋውንዴሽን፣ የአባይ ግድብና የ40/60 የቤቶች ግንባታ.” ሲሆኑ፣ ለነዚህ ማስፈፀሚያ “ገንዘብ አዋጡ” የሚለው ዋናው ግብ እንደነበር አስረድተዋል። በተለይ ደግሞ « በትግራይ ተወላጁ ዘንድ ሕወሐት የለም፣ ተከፋፍሏል፣ ተዳክሟል፣ ፓርቲው ሰው የለውም፤» የሚለውን እራሱ ቡድኑ በማንሳት ለገዛ ጥያቄው መልስ ሲሰጥ « ሕወሐት አሁንም ሃይል አለው፤ አልተዳከመም» በማለት አድራጊ- ፈጣሪ በመሆን ስልጣኑን በበላይነት ተቆጣጥሮ እንደያዘና ቡድኑ የመጣውም “አይዟችሁ” ለማለት እንደሆነ መገለፁን በቅርብ የተከታተሉት ምንጮች አስታውቀዋል። ቡድኑ በተጨማሪም ፥ « ልማት አልምተናል፤ ትግራይ እየለማ ነው፤ ህዝቡን ተጠቃሚ እያደረገነው ነው» ከማለቱ ባሻገር « በትግራይ ተወላጁ ላይ አደጋ ተደቅኗል፤ የሙስሊሙ፣ የትምክህተኞችና የሽብርተኞች አደገኛ እንቅስቃሴ እያንዣበበ መሆኑን፣…የተደቀነብህን አደጋ ከጎናችን ሆነህ ተከላከል፤ ያለበለዚያ ግን ሊያጠፉህ ነው፤» ሲሉ መናገራቸውን የገለፁት ምንጮች አክለውም፣ « አባላት የሆናችሁ ተወደደም ተጠላ መሬትና መኖሪያ ቤት እንሰጣችኋለን፤ ለዚህም ከእኛ ጎን መሰለፍ አለባችሁ» በማለት ሊሸነግሉ መሞከራቸውን ጠቁመዋል።

ከዋሽንግተን ስብሰባ (ለሁለት ተከፍሎ ነው የተካሄደው) በኋላ ወደ ሶስቱ ከተሞች ተከፋፍለው እንደሄዱ ሲታወቅ፥ ሲያትል አቶ ብርሃነ ማረት፣ እንዲሁም ላስቬስጋስ አባይ ወልዱና ተክለወይኒ አሰፋ መሄዳቸው ታውቋል። በተለይ በላስቬጋስ ጠንካራ ተቃውሞ የገጠማቸው እነአባይ ስብሰባው ከቀኑ 2፡00 ሰዓት ይጀመራል ተብሎ ከአራት ሰዓት በኋላ ዘግይቶ አመሻሽ ላይ መጀመሩን ምንጮች ገልፀዋል። ስብሰባው ሲጀመር ከላይ የተገለፁትን ጉዳዮች ያደመጠው ተሰብሳቢ ተከታዮቹን ጥያቄ አቀረበ፤ « ዴሞክራሲ አለ ትላላችሁ፣ ነገር ግን ዴሞክራሲ የለም፤ በሃሳብ የሚቃወማችሁን ታስራላችሁ፣ ታንገላታላችሁ፣ የሰብአዊ መብት ረገጣ ታካሂዳላችሁ፤ ከእናንተ የተለየ ሃሳብ ያለውን ትፈራላችሁ፤ ለምንድነው ይህን ሁሉ የምታደርጉት?….በማ.ረ.ት.(ማህበር ረድኤት ትግራይ) በትግራይ ሕዝብ ስም የምትሰበስቡትን ገንዘብ ለአራጣ ብድር እና ለፖለቲካ መጠቀሚያ በመሳሪያነት እያዋላችሁት ነው። ለምን?….ትእምት (ኤፈርት) ማነው ባለቤቱ?..በማን ነው የሚመራው?..ማነው የሚቆጣጠረው?..ለመሆኑ ኦዲት ተደርጎ ያውቃል ወይ?..እነማናቸው እየተጠቀሙበት ያለው?» የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ጥያቄዎች እንደነበሩ ምንጮቹ የጠቆሙ ሲሆን፣ አባይ ወልዱ « እኔ አልመልስም፣ ተ/ወይኒ መልስ ይስጥበት» ቢሉም ነገር ግን ግልፅና አግባብ ያለው ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ወደ ማመናጨቅና ቁጣ ያመሩት ተ/ወይኒ በዚህ ድርጊታቸው በርካታ ተሰብሳቢዎችን እንዳሳዘኑ አስረድተዋል። በዚህ የተበሳጨው ተሰብሳቢ « ጥያቄያችን አልተመለሰም» በማለቱና ሁከትና ያለመደማመጥ በማየሉ ስብሰባው እንዲቋረጥ መደረጉን የጠቆሙት ምንጮች፣ የጥያቄና ተቃውሞው መብዛት ያስደነገጣቸው ባለስልጣናቱ የመረጡት ማምለጫ በላስቬጋስ ተወካያቸው በሆነውና መድረክ ሲመራ በነበረው አቶ ተወልደ በኩል፥ « አዳራሹን የተከራየንበት ሰአት አብቅቷል፤ ስለዚህም ስብሰባው አብቅቷል » በማለት በአስቂኝ ሰበብ መቋረጡን አያይዘው ገልፀዋል። እነአባይ ከአዳራሹ ሲወጡ ቀድሞ ውጭ ሆኖ ይጠብቃቸው በነበረው ተሰብሳቢ ውግዘትና ስድብ እንደደረሰባቸው ያስታወቁት ምንጮች « ሌባ..ሌባ…ሙሰኞች..» የሚሉ ተቃውሞዎች ጎላ ብለው እንደተሰሙ አመልክተዋል።

ስብሰባዎቹን የታዘቡ ወገኖች በሰጡት አስተያየት እንዲህ ብለዋል፤ « በአንድ በኩል ልማት እያካሄድን ነው፤ እያሉና ገንዘብ እየጠየቁ በሌላ በኩል “ትግራዋይ አደጋ ተደቅኖብሃል፣ ከጎናችን ሆነህ ተከላከል፤” ማለት እርስ በርሱ የሚጋጭና ድጋፍ የማግኛ የፖለቲካ የፖለቲካ ቁማር ነው። ያልተጠየቁትን የፓርቲውን ህልውና (ስለ ሕወሐት) አንስቶ መነገሩም አስገራሚና አጠያያቂ ነው።» ሲሉ ትዝብታቸውን የጀመሩት እነዚህ ወገኖች በማያያዝም፥ « እነዚህ ሰባት ባለስልጣናት ወደ አሜሪካ የመጡት ከነዘመዶቻቸው፣ ጋሻ ጃግሬዎቻቸው ሲሆን፣ ባለስልጣናቱ የመንግስት ወኪሎች እንደመሆናቸው – በማን ገንዝብ ነው የሚንቀሳቀሱት?..የሚለው መጠየቅ አለበት። በሕዝብ ገንዝብ እየተንፈላሰሱ እንደሆነ ግልፅ ነው። የትግራይ ተወላጁን ብቻ ለይተው ስብሰባ የሚጠሩት ለምንድነው?…በእርግጥ ስላሰቡለት ነው?…የሚሉት ሲፈተሹ .መልሱ በጭራሽ አይደለም ነው። አላማቸውና ትኩረት የሰጡት የትግራይ ተወላጁን እየተንከባከቡት እንደሆነና ተጠቃሚ መሆኑን ለማሳየት በመፈለግ፣ እግረ-መንገዳቸውን ከቀሪው ኢትዮጲያዊ ወገኑ ጋር በመነጠል..ድጋፍ ለማግኘትና በውስጣቸው የተፈጠረውን ቀውስ በዚህ በኩል ቀዳዳውን ለመድፈን የሚደረግ የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ ስልት ነው። ..ደግሞስ ሕወሐት “አጋር” ከሚላቸው ብ.አ.ዴ.ን፣ ኦ.ህ.ዴ.ድ.፣ ደቡብ ሕዝቦች ተለይቶ፣ በሕዝብ ገንዘብ ስብሰባ የሚጠራበትና ያሻውን የሚያደርግበት አግባብ ምንድነው?..የሚለው ከዚህ ጋር መታየት ያለብት ነው። ፖለቲካዊ ፍጆታና ማንአለብኝነት በፓርቲው በመነገሱ እንደሆነ ደግሞ ግልፅ ነው።» ብለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፥ አሜሪካ ከመጡት ሰባት የሕወሐት ባለስልጣናት መካከል- ማለትም አባይ ወልዱ፣ ብርሃነ ኪ/ማሪያም፣ ተ/ወይኒ አሰፋና ዳንኤል አሰፋ በዋነኛነት ሲጠቀሱ፣ ከሰባቱ ሶስቱ ስብሰባውን ሳያካሂዱ ከቡድኑ ተገንጥለው በአሜሪካ መቅረታቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል። ቤተሰቦቻቸውን ይዘው (ልጆቻቸውን ጭምር) በመምጣት አሜሪካ ጥገኝነት ጠይቀው መቅረትን የመረጡት ባለስልጣናት ውስጥ የሕወሐት ማ/ኮሚቴ አባላት እንዳሉ ያረጋገጡት ምንጮች በቅርቡ ዝርዝሩን ይፋ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።

 

 

በፍቼ በአንድነት ፓርቲ አባላት ላይ የደረሰ ድብደባ

የኢሕአዴግ ወታደራዊ ትጥቅ ማምረቻ ፋብሪካ ተቃጠለ

$
0
0

(ይህን የሚሊተሪ ልብስ የሚያመርተው ፋብሪካ ነው የተቃጠለው)

(ይህን የሚሊተሪ ልብስ የሚያመርተው ፋብሪካ ነው የተቃጠለው)

በመከላከያ ሚኒስትር የትጥቅና ወታደራዊ ልብስ ስፌት ፋብሪካ ህንጻ ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የአይን እማኞች ማስታወቃቸውን ኢሳት ራድዮ ዛሬ ዘገበ። የእሳት አደጋ ቃጠሎ በሕንፃው ላይ ጉዳት እንዳደረሰና እንዳወደመ የዘገበው ኢሳት ራድዮ የአደጋውን ምንጭ እያጣራሁ ነው ብሏል።
ከአዳማ ከተማ ወደ ወንጂ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው ወታደራዊ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ በፋብሪካው ላይ ከፍተኛ የንብረት ጉዳት መድረሱን የዘገበው ራድዮው በ18 ሚሊዮን ብር ወጪ በቅርቡ የተገነባው ፋብሪካው የተለያዩ ወታደራዊ ዩኒፎርሞችን ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ የሚያቀርብ ሲሆን የደረሰው አደጋ መንስኤ ሊታወቅ አልቻለም ብሏል።
እንደ ራድዮው ዘገባ ከሆነ በፋብሪካው ላይ የደረሰውን ቃጠሎ ለማጥፋት ከአዳማ ከተማ የእሳት ማጥፊያ ባለመኖሩ ደብረ ዘይት ከሚገኘው አየር ሀይል እሳት ማጥፊያ እስከሚደርስ ድረስ የተነሳውን እሳት ማጥፋት አለመቻሉን የአይን እማኞች ተናግረዋል፡፡ ለአንድ ሰዓት ያህል በቆየው የእሳት አደጋ ግምታቸው ከፍተኛ የሆነ ማሽኖች ላይ ጉዳት እንደደረሰ የታወቀ ሲሆን ከአራት ቀናት በፊት መንግስት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የገዛቸው ማሽኖች በፋብሪካው ገብተው እንደነበረ ታውቋል ሲል ኢሳት ራድዮ ዘገባውን አጠናቋል።

ከአደጋው በስተጀርባ ሊደበቅ የተፈለገ የሙስና ወንጀል ይኖር ይሆን?

Sport: ሳሙኤል ኤቶ ቸልሲ ገባ

$
0
0

samuel eto(ዘ-ሐበሻ) አንዴ ይወጣል አንዴ ይቀጥላል በሚል ሲያወዛግብ የነበረውን የማን.ዩናይትድ አጥቂ ዋይኒ ሩኒን “በ24 ሰዓታት ውስጥ ወደ ቸልሲ መግባት አለምግባቱን እንዲያሳውቅ” የቸልሲው አለቃ ሆዜ ሞሪንሆ የጠየቁ ቢሆንም ለሩኒ ያቀረቡት የ24 ሰዓት ገደብ ሲያልቅ ወዲያውኑ ካሜሩናዊውን አጥቂ ሳሙኤል ኤቶን አስፈርመዋል።
የቀድሞው የባርሴሎና ኮከብ ሳሙኤል ኤቶ በቸልሲ ከረዥም ዓመታት በፊት ጀምሮ ሲፈለግ የነበረ ቢቆይም ዝውውሩ እስካሁን ሳይሳካ ቢቀርም አሁን ግን ተጫዋቹ ወደ እርጅና እየተጠጋ ባለበት ጊዜ ከሩሲያው ክለብ አንዝሂ ማካቻካል አስፈርሞታል።

ከ እንግሊዝ ሚዲያዎች አካባቢ ከቃረምናቸው መረጃዎች እንደተረዳነው ቸልሲ የሳሙኤል ኤቶን ስምምነት በነጻ ዝውውር የፈጸመ ሲሆን ውሉም ለአንድ አመት የሚቆይ ይሆናል። ሳሙኤል ኤቶ ወደ ሩሲያው አንዚ ማካቻካላ የተዛወረው በ€21ሚሊዮን ሲሆን ዓመታዊ ደሞዙ ደግሞ €10ሚሊዮን ነበር። አሁን ከቸልሲ ምን ያህል እንደሚያገኝ የተቃረመ ነገር አላገኘንም።

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live