Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

አቡነ ማትያስ መህበረ ቅዱሳንን አፈርሰዋለው ሲሉ የማፍረሻውን ትዕዛዝ ማን ሰጣቸው? ቅዱስ ሲኖዶስ? ወይንስ….? |ከተማ ዋቅጅራ

$
0
0

ያልፈረሰን ማፍረስ ያልተነቃነቀን ማነቀነቅ በአንድነት ለዘመናት ተዋደው እና ተፋቅረው የኖሩትን ህዝብ መበተን የኢትዮጵያኖች የእለት ተእለት ዜና ከሆነ ስንብቷል። ዛሬም በአንድነት እና በጥንካሬአቸው ለቤተ ክርስትያን እውቀታቸውን፣ ገንዘባቸውን፣ ጉልበታቸውን ሳይሳሱ በመስጠት የቤተክርስትያን ልጅነታቸውን በማስመስከር ያልተማረን እንዲማሩ በማርደግ፣ የአብነት ትምህርት ቤቶችን ህንጻዎችን በማነጽ እንዲጠናከር በማድረግ፣ ቤተክርስትያንን በቅንነት በማገልገል ወጣትነት ሳያታልላቸው በጉብዝናህ ግዜ እግዚአብሔርን አስብ የሚለውን አምላካዊ ቃል እየፈጸሙ ያሉትን ወጣቶች የበለጠ ፍቅር፣ የበለጠ አባታዊ ምክር፣ የበለጠ ቤተ ክርስትያኗ ድጋፍ፤ ማድረግ ሲገባቸው የቤተክርስትያኗ መሪ በተባሉት በአቡነ ማቲያስ የሰላ ትችት እየተሰጣቸው እጅና እግራቸውን አስሬ ካላስቀመጥኳቸው ተብሎ ዛቻዎችን ስንሰማ እንደ ቤተክርስትያን ልጅነታችን የሚያም ጉዳይ ነው። ማን አይዞት ብሎዎት ነው የቤተክርስትያን ልጆችን ለማሰር የተነሱት? የየትኛውስ አካል ለማስፈጸም ነው ማህበረ ቅዱሳንን ለማፍረስ የተነሱት?
H_E_Abune_Matiyas_Archbishop_of_Jerusalem_Misa

የማህበረ ቅዱሳን አባል ከአለማዊ ትምህርት የአለማዊ ትምህርታቸውን ጠንቅቀው የተማሩ ከመንፈሳዊ ትምህርታቸውም መንፈሳዊ ትምህርታቸውን በደንብ የተማሩ የተማሩትንም በስራ ላይ የሚያውሉ በአባቶች መሰረት ላይ የተመሰረቱ የቤተክርስትያን አገልጋዮች ናቸው። ማህበረ ቅዱሳን በቁጥር በጣም ብዙ የሚባል አባል እንዳለው የሚታወቅ ሲሆን አገልግሎታቸውም እንደ ቁጥራቸው በጣም ሰፊ ነው። በመላው ኢትዮጵያ የሲኖዶስ አባቶች ሊደርሱበት ያልቻሉትን ቦታዎች ጭምር በመድረስ የቤተክርስትያን ልጅነታቸውን በማስመስከር የተዘጉ ቤተክርስትያንን በማስከፈት፣ ሊዘጉ ያሉትን ሳይዘጉ በመድረስ በተጠናከረ ሁኔታ ቀጣይነት ባለው መልኩ አገልግሎት እንዲቀጥል በማድረግ ቋሚ መገልገያ በመትከል እራሳቸውን በራሳቸው የሚያስተዳድሩበትን ስራ በመስራት ከፍተኛ ተጋድሎ እያደረጉ ያሉ የቤተክርስትያን ልጆች ናቸው።

የማህበረ ቅዱሳን እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን በመላው አለም የተዘረጋ በግዜ እና በቦታ ሳይወሰኑ ለቤተክርስትያን ቅድሚያ በመድረስ አገልግሎት በመስጠት ያለ ስብስብ ነው። ቅዱሳኖች ግዜአቸውን፣ እውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውን ለቤተክርስቲያን በመስጠት ከእግዚአብሔር የአገልግሎታቸውን ዋጋ የጽድቅ አክሊል ተቀብለዋል። የስሙ ስያሜውም እንደሚነግረን የማህበረ ቅዱሳን አገልግሎት ከዚህ የተለየ ባለመሆኑ ማህበረ ቅዱሳን ተብሏል። የቅዱሳንን ፈለግ ተከትለዋልና።

ታዲያ አቡነ ማቲያስ ማህበረ ቅዱሳንን ማፍረስ ለምን አስፈለጋቸው? እውነተኛ አባት ቢሆኑ ልጆቻቸው በቤተ ክርስትያን ተሰብስበው ሲያዮ ደስ ሊላቸው ሲገባ… ልጆቻቸው ተሰብስበው ስለቤተክርስትያን በአንድነት ሲቆሙ ሊያኮራቸው ሲገባ… ልጆቻቸው ገንዘባቸውን፣ እውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ሳይሳሱ ለቤተክርስትያን ሲሰጡ ሊኮሩባቸው እና የበለጠ እንዲተጉ ሊያበረቷቷቸው ሲገባ አስሬአቸው እነሱን ሳላጠፋ እንቅልፍ አይወስደኝም ተብሎ መዛቱ ከፓትሪያሪክ የሚጠበቅ ነውን? ሲኖዶሱ ልጆቻቸው እጅና እግራቸው ታስሮ ከቤተክርስትያን መጥፋት አለባቸው ተብለው ሲዛትባቸው የማህበሩ አባላት ካልጠፉ እንቅልፍ እንደማይተኝ ሲነገርባቸው ምን ተሰምቷችሁ ይሆን?

ሲኖዶስ ከዚህ በፍት አቡነ ማትያስ ላይ በማህበረ ቅዱሳን እና በሌላ ቤተክርስትያናዊ ጉዳዮች ላይ አቡኑ በግላቸው ጥቂት ግለሰቦችን ሰብስበው ከሳቸው ጋር እንዲቆሙ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ላይ ጠንካራ አቋም በማሳየት የአቡኑን ሃሳብ በሙሉ ውድቅ በማድረግ ጥንካሬአቸውን አይተናል። እኛም በእውነተኛ አባቶች በሲኖዶሱ ውሳኔ እጅጉን ኮርተናል። ዛሬ ለምን ተመልሶ መጣ? ተመልሶ ሲመጣስ የሲኖዶስ ውሳኔ ምን ይሆን? ወደፊትስ ተመልሶ እንዳይመጣ ምን አይነት ውሳኔ ይሆን የሚወሰነው?

እንደ ቀልድ በሚሊዮን የሚቆጠር ስብስብን እግሩን እና እጁን አስረዋለው ብሎ መናገር ከቤተክርስትያን አባት ይጠበቃልን? የአባቶች ድርሻ እኮ ያልተሰባሰቡትን ወደ ቤተክርስትያን መሰብሰብ እንጂ በቤተ ክርስትያን ስር የተሰበሰቡትን ከቤተክርስትያን ማባረር አይደለም። በእግዚአብሔር ቤት ላይ ሹመት የተቀበላችሁት በቤተክርስትያን ጥላ ስር የተሰበሰቡትን ለማፍረስ እና ለመበታተን ነው እንዴ? በእውነተኛዋ ቤተክርስትያን ስር በፍቅር ተሰብስበው በጥላዋ ያረፉትን እንደ ሰው ፍላጎት በቀላሉ ማፍረስስ ይቻል ይሆንን? በቤተክርስትያን ስር ያለመለያየት በአንድነት የተሰበሰቡትን የቤተክርስትያን ልጆችን አፈርሳችኋለው ብሎ መናገር የቤተክርስትያን አባቶች ሃሳብ ወይንስ የሌላ አካል ሃሳብ?

አቡነ ማቲያስ መሐበረ ቅዱሳንን አፈርሰዋለው ብለው ይናገሩት እንጂ ከኋላቸው ማን እንዳለ የታወቀ ነው። ማህበረ ቅዱሳን ያሰባሰባቸው ሁሉም የቤተክርስትያን ልጆች መሆናቸው ብቻ ነው። የማህበሩ አባል የሚሆነው ወይንም የሆኑት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኝ የሆነ ብቻ ነው። ምንም አይነት የፖለቲካ አላማ የሌለው ማህበር ነው። የዘር የቀለም ልዩነት የለም።በእርግጠኛነት ለመናገር ከሁሉም ብሄሮች ውስጥ የተዋህዶ ልጅ ከሆነ የማህበሩ አባል መሆን የፈለገ መሆን ይችላል። ወደዚህ ማህበር ሲመጣ ስለ ብሔር ወይንም ስላለህ ፖለቲካ አመለካከት ቦታ የለውም። ምክንያቱም የማህበሩ ምስረታ ምድራዊ መንግስትን ለማገልገል ሳይሆን ሰማያዊ መንግስትን መስበክ ስለሆነ። ምድራዊ ስልጣንን ለማስገኘት ሳይሆን የማታልፈውን የእግዚአብሔር መንግስት ለማውረስ ስለሆነ። ስለዚህ የሐጥያት ስር የሚባሉት ዘረኝነት፣ ወገኝተኝነት፣ገንዘብ ወዳድነት፣መለያየት የመሳሰሉት በማህበሩ ውስጥ ቦታ የሚሰጣቸው ጉዳዮች አይደሉም። ስለዚህ እውነተኛ ኢትዮጵያዊነት እና የእግዚአብሔር አገልጋዮች የሚገኙበት ማህበር ነው። ከየትም ይምጣ ከየት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጅ ከሆነ የዚህ ማህበር አባል መሆን ይችላል። ማህበሩን የማታውቁት አለ ብዬ መናገር ባልደፍርም ካላችሁ ግን ያለው እውነት ይሄ ነው።

ማህበረ ቅዱሳንን ማፍረስ የተፈለገበት ዋናው አላም ለመንግስት ፖሊሲ የተመቸ ስላልሆነ ነው። እንደ መንግስት ሃሳብ በዘር የተደራጀ ቢሆን ኖሮ አልያም የመንግስት ደጋፊ ሆነው መንግስት የሚፈልገውን የማለያየት ስራ የሚሰሩ ቢሆኑ ኖሮ ወይንም እንደ መንግስት ሃሳብ ኢትዮጵያን የማፍረስና ታሪኳን የማጥፋት ስራ የሚሰሩ ቢሆኑ ኖሮ የኦርቶዶክስ አማኝ በሙሉ ወደዚህ ማህበር እንዲገቡ መንግስት ያስገድድ ነበረ። ይሄ ባለመሆኑ ዘረኝነት የእግዚአብሔርን መንግስት አይወርስም ታሪካችንንም ለአፍሪካ ብሎም ለአለም ህዝብ ምሳሌ ነው በማለት አንድነት፣ ፍቅር፣ የእግዚአብሔር መንግስት የሚሰበክበት ማህበር በመሆኑ ዘረኝነት ነብሳቸው ትጸየፋዋለች ጥላቻንም አያስተምሩም ፍቅር ቤታችው፣ ፍቅር አገራችው፣ ፍቅር አምላካችው ነው በመሆኑ መንግስት ለማፍረስ ተነሳ። እንደተለመደው መንግስት እጄ የለበትም ለማስባል ሁሉንም በራሳቸው ሰዎች ከኋላ ሙሉ ድጋፍ በመስጠት የሚያስመታው። ነገሮች አቅጣጫውን ስተው ጠንካራ ተቃውሞ ገጥሞት መቀልበሻው ሲጠፋውና ሲጨንቀው ደግሞ እርቅ ይላል። አቡነ ማቲያስ በማህበረ ቅዱሳን ላይ የመነሳታቸው ሚስጢር 100% የመንግስት መዶሻ ሆነው ማህበሩን ለመምታት የተነሱ አባት ናቸው እንጂ ለቤተክርስትያን በመቆርቆር ከቤተክርስትያን አባቶች ጋር ተማክረው የቤተክርስትያንን መሰረቷን ለማጥበቅ የተነሱ እንዳልሆነ ጥንቅቀን እናውቃለን።

የቤተክርስትያንን ህልውና የሚፈታተንና ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነገር ከፊታችን ቀርቧል እኛ ልጆቿ ከእግዚአብሔር ዋጋ የምናገኝበት አልያም የምናጣበት።
ይሄንን ሁላ የምለው የማህበረ ቅዱሳን አባል ሆኜ አይደለም ነገር ግን እንደ ቤተክርስትያን ልጅኔቴ የቤተክርስትያን ጉዳይ ስለሚያገባኝ ነው። ስለ ቤተክርስትያን ጉዳይ ዝም ማለት አየር ሳትተነፍስ መኖር አንድ ነው። ስጋዊ ህይወትህ ማኖር ካለብህ ለደቂቃም ማጣት የማትችለው ነገር አየር ነው። ነፍስህን ለዘላለም በእግዚአብሔር እቅፍ ማኖር የምትችለው ቤተክርስትያን ስትኖር ብቻ ነው። ስለዚህ ስለ ቤተክርስትያን ዝም አንልም።
ከተማ ዋቅጅራ
28.01.2016
Email- waqjirak@yahoo.com

The post አቡነ ማትያስ መህበረ ቅዱሳንን አፈርሰዋለው ሲሉ የማፍረሻውን ትዕዛዝ ማን ሰጣቸው? ቅዱስ ሲኖዶስ? ወይንስ….? | ከተማ ዋቅጅራ appeared first on Zehabesha Amharic.


በነጆ የተገደለው ገመቹ ጥላሁንን ለመቅበር የወጣውን ሕዝብና ቁጣውን የሚያሳይ ቪዲዮ

$
0
0

በኦሮሚያ ክልል የተነሳው ሕዝባዊ ቁጣ በተለያዩ ቦታዎች በቀጠለበት ሁኔታ አሁንም የአጋዚ ሰራዊት ሰላማዊ ታጋዮችን መግደሉን ቀጥሏል:: ቀጣዩ ቪዲዮ የሚያሳየው በነጆ ከተማ በወያኔ ሠራዊት የተገደለው ገመቹ ጥላሁንን ለመቅበር የወጣውን ሕዝብ እና ቁጣውን ነው::

The post በነጆ የተገደለው ገመቹ ጥላሁንን ለመቅበር የወጣውን ሕዝብና ቁጣውን የሚያሳይ ቪዲዮ appeared first on Zehabesha Amharic.

ምናልባት ስለሞጋቾች ድራማ ምርጥ አርቲስቷ ፍቅርተ ደሳለኝ የማታውቋቸው ነገሮች

$
0
0

Screen Shot 2016-01-28 at 11.02.40 AM

አርቲስት ፍቅርተ ደሳለኝ  አዲስ አበባ ውስጥ ቀበና አካባቢ ነው ተወልዳ ያደገችው፡፡ ወደ ሙዚቃው አለም ስትገባም የብዙነሽ እና የሂሩት በቀለ ስራዎችን በማንጎራጎር ነበር፡፡ ይህ ግንኙነትም ተጠናክሮ በናይጄሪያ ሎጎስ እና በሱዳንም ስራዎቻቸውን አብረው አቅርበዋል፡፡ በ1958ዓ.ም የቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለስላሴ (የአሁኑ ብሄራዊ ቲያትር) በድምፃዊነት ከመቀጠሯ አስቀድሞ በምሽት ክበብ ውስጥ ትሰራ ነበር፡፡ብሄራዊ ቲያትር የገባችውም በቴሌቭዥን ስትዘፍን የተመለከቷት የዛን ጊዜው የብሄራዊ ቲያትር ስራ አስኪያጅ ችሎታዋን አድንቀው ወደ ቲያትር ቤቱ እንድትመጣ በመጠየቃቸው ነበር፡፡በወቅቱ የተሰጣትን ፈተና በአጥጋቢ ሁኔታ በማለፏ በ100 ብር ደምወዝ ተቀጠረች፡፡
722fikirtedesalegnoldies

በአንድ ወቅት ስራዋን በቀጥታ ስርጭት ስታቀርብ የዘፋኝ ስም ሲፃፍ የአባቷን ስም ቀይራ ነበር፡፡ ከቤተሰቦቿ ለመደበቅ እና በወቅቱ በድምፃውያን ላይ ይሰነዘር ከነበረው ትችት ለመሸሽ ስትል እንደሆነም ትናገራለች፡፡ እናም በጊዜው ፍቅርተ ደሳለኝ የነበረ ስሟ ፍቅርተ ግርማ ተብሎ በቴሌቭዥን በመታየቱ በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ ሆና ነበር፡፡ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ቲያትር ቤትን በተቀላቀለችበት ጊዜ ቲያትር ቤቱ በስሩ 3 ኦርኬስትራዎች ነበሩት (ያሬድ፣ ዳዊት፣ እዝራ) ፡፡ አርቲስት ፍቅርተ ደሳለኝም በያሬድ ኦርኬስትራ ስር ሆና የተለያዩ የሀገራችን ክፍል ተዘዋውራ ሰርታለች፡፡
ከሰራቻቸው ዘፈኖቿ መካከል ጥቂቶቹን እናንሳ፡- የሻለቃ ግርማ ሀድጎ ግጥም እና ዜማ የሆነው የመጀመሪያ ስራዋ “የፍቅር ምድጃ”፣ “ሰው በናፍቆት አይሞትም”፣ “ኮተት” የተሰኘው የሲራክ ታደሰ ድርሰት፣ “ቤትም እኮ ነበር”፣ “የመኖሬ ተስፋ”፣ “የኔ አለኝታ”፣ በ1963ዓ.ም የተቀረፀው “ባሌ ነው ህይወቴ”፣ በጎዳና ተዳደሪ ልጆች ላይ የሚያተኩረው እና ከታምራት አበበ ጋር የተጫወተችው “ጠውላጋዋ አበባ”፣ እንዲሁም ከጌጡ አየለ ጋር በርካታ አስቂኝ የኮሜዲ ሙዚቃዎችን ተጫውታለች፡፡

10698681_10203742346733155_4838225161140564847_n   ፍቅርተ ደሳለኝ እና ጌጡ አየለ በሚሰሯቸው የኮሜዲ ሙዚቃዎች አቀራረባቸው ከስሜት ጋር ነበር፡፡ በጊዜውም ባልናሚስት፣ እጮኛሞች፣ ፍቅረኛሞች እና መሰል ገፀ ባህሪያትን ወክለው ስለሚጫወቱ በተመልካች ዘንድ ባልና ሚስት ተደርገው ይቆጠሩ ነበር፡፡ እንደ አርቲስቷ ገለፃ “አርቲስት ጌጡ አየለ የወንድ ጓደኛ እንኳን አልነበረውም፡፡ ሰርጉንም እኔ ነኝ ደግሼ የዳርኩት” በማለት በሁለቱ መካከል ያለውን ግንኙነት ታስረዳለች፡፡
ቀደም ሲል ትምህርት ሳትማር የትራንፔት ተጫዋች የሆነው የመጀመሪያ ባለቤቷ አቶ ግርማ ገብረአብ እያስጠናት በግሩም ሁኔታ ዘፈኖቿን ታቀርብ ነበር፡፡ ባለመማሯ የተቆጨችው ፍቅርተ ደሳለኝ በየነ መርዕድ የማታ ትምህርቷን ጀምራ ፍሬህይወት 1ኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ 8ኛ ክፍል ተማረች፡፡ ከዚያም በሌላ ት/ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ትምህርቷን አጠናቃቀች፡፡
አርቲስት ፍቅርተ ደሳለኝ ከሙዚቃዎቿ ባሻገር በርካታ ትያትሮችና እና ፊልሞችን ሰርታለች፡፡ ከሰራቻቸው ትያትሮች ውስጥ የሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን የትርጉም ስራ የሆነው “የፌዝ ዶክተር ” የተሰኘው ትያትር የመጀመሪያ ስራዋ ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ “ጥላ”፣ “የባላገር ፍቅር”፣ የዶ/ር አርቲስት ተስፋዬ አበበ ድርሰት የሆነው “አምታታው በከተማ” ላይም የገጠር ሴትን ወክላ ተጫውታለች፡፡ በ1992ዓ.ም ጡረታ ከወጣች በኋላ የአዜብ ወርቁ የትርጉም ስራ የሆነው “8ቱ ሴቶች” እንዲሁም “ፍቅር የተራበ” ትያትር ላይ ተውናለች፡፡

ከትያትሩ ወደ ፊልም ኢንዱስትሪው ተቀላቅላ በዛ ያሉ ፊልሞች ላይም ሰርታለች፡፡ ለአብነትም ፡- “ማራ፣ ማንነት፣ ታስራለች፣ ዱካ፣ የህሊና ዳኛ/ የመጀመሪያ የፊልም ስራዋ ነው/፣ ቫኬሽን ፍሮም አሜሪካ፣ ሰርፕራይዝ፣ ጥቁር ነጥብ፣ የልደቴ ቀን፣ ያ ልጅ፣ የትውልድ እንባ፣ ስሌት፣ ጓንታናሞ፣ ልዩነት፣ 400 ፍቅር፣ አይራቅ፣ ጉደኛ ነች የመሳሰሉትን በጥቂቱ መጥቀስ ይቻላል፡፡ አርቲስት ፍቅርተ ደሳለኝ በትያትርም ሆነ በፊልሞቹ ላይ ብዙውን ጊዜ የእናት ገፀ ባህሪን ተላብሳ ነው የምትቻወተው፡፡
ለመድረክ ከፍተኛ ክብር የምትሰጠው አርቲስት ፍቅርተ ደሳለኝ ሽቅር ቅር እና ሳቂታ ናት፡፡ ፈገግታ ከፊቷ የማይለያት አርቲስቷ እንባዋም ቅርብ ነው ይላሉ በቅርብ የሚያውቋት ጓደኞቿ፡፡ ጡረታ በ1992ዓ.ም ከወጣች በኋላ የፍቅር ዘፈን አልሰራም፤ ከሰራሁም ጠንከር ያሉና አስተማሪ ስራዎችን ነው የምሰራው የሚል አቋም አላት፡፡

Screen Shot 2016-01-28 at 11.07.04 AM
አርቲስት ፍቅርተ ደሳለኝ ከትራንፔት ተጫዋች ባለቤቷ ከአቶ ግርማ አንድ ልጅ ወልዳለች፡፡ ይህ ትዳር ባይዘልቅም አሁን ሌላ ትዳር መስርታ እና ልጆች ወልዳ እየኖረች ነው፡፡ የልጅ ልጅ ያየችው እና የአራት ልጆች እናት የሆነችው ፍቅርተ ደሳለኝ በቅርቡ የወጡ እና ሊወጡ የሚችሉም በርካታ ፊልሞችም አሏት፡፡ የተለያዩ የቴሌቭዥን ድራማዎች ላይም ተሳትፋለች፡፡
ለአንጋፋዋ ድምፃዊት እና ተዋናይት እድሜ እና ጤና ተመኘሁ፡፡

The post ምናልባት ስለሞጋቾች ድራማ ምርጥ አርቲስቷ ፍቅርተ ደሳለኝ የማታውቋቸው ነገሮች appeared first on Zehabesha Amharic.

“በአኮቦ ወረዳ ከ200 በላይ የሚሆኑ አኙዋኮች ህፃናት እና ሴቶች ተጨፍጭፈዋል”–ከታህሳስ ሶስት መታሰቢያ ዲሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ የተሰጠ መግለጫ

$
0
0

ከታህሳስ ሶስት መታሰቢያ ዲሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ የተሰጠ መግለጫ

(December 13 Commemoration Democratic Movement)

ጥር 16 ቀን 2008 ዓ.ም

ሁላችንም እንደምንገነዘበው ባለፋት 25 አመታት ወያኔ ሲጠቀምባቸው የነበሩ ስሌቶችና ጭካኔና በተሞላበት ድርጊቶች መካከል የኢትዮጵያን ህዝብ በዘር በሀይማኖት እና በክልል እየከፋፈለ አንዱን ብሄረስብ በሌላው ላይ እያነሳሳና እያስታጠቀ ለመቆየት በመቻሉ ነው። በተናጠል ሌላውን ብሄረሰብ እያጠቃ በጠቅላላው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚፈፅመው የኢሰብዓዊ ድርጊቶች ከማንኛውም ግዜ በላይ በመቀጠል ላይ ነው ያለሁ። ለዘመናት በሰላም እና በፍቅር ይኖር የነበሩትን ብሄረሰቦች እርስ በእርስ በማጋጨት በሌላው ብሔረሰብ ላይ የዘር ማጥፋት ዘመቻም እያወጀና እየጨፈጨፈ ሲያንስም የሕዝቡን ነፃነት እየሸረሸረ ዛሬ በበለጠ ግዜ የሀገሪቷን ሉዓላዊነት አወዛጋቢ ሁኔታ ላይ ጥሎዋታል።

File Photo

File Photo

መላው የአለም ህዝብ እንደሚያውቀው ታህሳስ 3፣1996 ዓ.ም (December 13, 2003) በጋምቤላ ከተማና በተለያዩ ወረዳዎች ዉስጥ ከሶስት ሺህ በላይ የሚበልጡ እኙዋኮች እንደ እንስሳ በወያኔ የታደኑበት ቀን ነች። ይህን ድርግት በተመሣሣይ ሁነታ በሌላው የኢትዮጵያ ብሕረሰብ ላይ እንዳይደገምና መላዉ የአለም ሕዝብ ይህን ታርካዊ ቀን እንድያስታውሳትና እንዳይረሱት ምክንያት ተደርጎ ይህንን ድርጅት በዚቹ ቀን እንድሠየም ተደርጓል። አሁንም ቢሆን በአኙዋኮች ላይ በሌላ መልኩ ተመሳሳይ ግድያ እየተካሄደ ነው። ባለፈው ወር ብቻ በአኮቦ ወረዳ ከ200 በላይ የሚሆኑ አኙዋኮች ህፃናት እና ሴቶችን ጭምር ወያኔ ባስጣጠቃቸው ከባድ የጦር መሳሪያዎች በስደተኛው ንዋር ብሄረሰብ ተጨፍጭፈዋል። እንዲሁም አኮቦ ወረዳ አልፎ በተመሳሳይ ሁኔታ ደግሞ በኢታንግ ወረዳ የሚገኙ ቀበሌዎች በነዚህ የጦር መሣርያዎች በመደብደብ በርካታ በቶችና ንብረቶችን ተጋይተው 18 በላይ የሚበልጡ አኙዋኮች መገደላቸው እና በርካቶች መቁሰላቸው ለአለም ተገልፆዓል።

በተጨማሪ አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝና የተቀሩት ከፍተኛ የወያኔ ባለሥልጣን በተገኙበት ለውሸት ፕሮፓጋንዳ ተብሎ በጋምቤላ የብሄርና ብሄረስቦች በሚከበርበት ቀን ለአኙዋኮች መግደያ እንዲሆን የታቀደው የጦር መሳሪያ የተከማቸበት ግምጃ ቤት እንዳይከፈት በትህዛዛቸው የተከለከለ ሲሆን ፣ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ እነዚህን መሳሪያዎች ለአጋሩ የንዋሩ ብሕረሰብ ለማከፋፈል ስሞክሩ የጫኑበት መኪና ላይ በኬላ ላይ በመያዙ እስከ ዛሬ ድረስ ማንም በዚሁ ሽብር የተጠየቀ እንዳልነበረ ነው። በአለፋት ቀናት በዜና ምንጮች ስዘገቡ የነበረው የጋምቤላ አሳሳቢ ሁኔታ የንዋሩና የወያኔ ሴራዎች በመሆናቸዉ የአኝዋክ ብሕረሰብ ለዘመናት በዘግነቱ የኮራ ለአገሪቷን ሉዑላዊነት ከሚገባው መጽዋትነት የከፈለ በወያኔ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ያልተበገረ አኩሪ ታሪክ ያለው ሕዝብ ነው። ይህን ሆኖ እያለ ወያኔና ግብረአበሮቹ የአቀዱትን የአኝዋኩ ብሕረሰብ የመጨፍጨፍ ሴራ ማንኛውም ኢትዮጵያዊና የአለም ሕብረተሰብ በጥብቅ እንድያወግዘውና እንድያከሽፍ ያስፈልጋል። በመቀጠልም በአዲስ አበባ አካባቢ የሚገኙ የታወቁ እና ያልታወቁ አስቃቂ እስር ቤቶች ክ200 በላይ የሚሆኑ አኙዋኮችና የመጀንገር ብሄረስብ ሀባላት በታህሳስ 3፣ 1996 ዓ.ም ወያኔ በፈፀመው የዘር ማጥፋት ወንጄል በግድያ ወቅጥ በመትረፋቸው ብቻ ተወንጅለው በእነዚህ እስር ቤቶች በመሰቃየት ላይ ናቸዉ።

ትላንት በአማራው በሱማሌው በኦሮሞው በአኙዋኩ በመጀንገር እና በሌሎችም የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ሲፈፀም የነበረው ግድያ፣ አሁንም ደግሞ በአዲስ አበባ ማስተርፕላን ጋር የተያያዘው ህዝባዊ እንቅስቃሴ ሰበብ በማድረግ የወያኔ አሸባሪ ሰራዊት የኢትዮጵያ ህዝብ ጭካኔ በተሞላበት ጭፍጨፋ የተፈፀመባቸዉ ናቸው። ከዚህም አልፎ የሀገሪቷን ንብረቶች እየዘረፈ፣ መሬቶችን እየነጠቀ እና ህዝቡን በማፈናቀል ለ25 ዓመታት ሁሉ የዘረጉትን የግድያ ስንስለቶች እንዲቆይ ያደረገው ህዝብን በመከፋፈል መሆኑ እየታወቀ አሁን ኦሮሞ ሕዝብ ለነፃነትና ለእኩልነት የሚያካሆደሁን እንቅስቃሴ የአንድ ብሄረሰብ ትግል ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድነትን የተመረኮዘ ትግል እንደሆነ ሊታሰብበት ይገባል ።እስከ ዛሬ ድረስ ወያኔ በሌላውብሄረሰብ ላይ በጠናጥል ሲፈፅማቸው የነበሩትን ግድያዎች በጠቅላላው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እንዳልተፈፀመ ተደርጎ ባለመወሰዱ የወያኔ አረመኔነትን እንድያራዝም አድርገናል። በመሆኑም ይህች አገር ከገባችበት ሰቆቃ ለማላቀቅ የመላው የኢትዮጵያ ብሄረስቦች በአንድነት በዘር በሀይማኖት ሳይከፋፈሉ ሁሉን ያካተተ ውህደት በመፍጠር ወያኔ የሚወገድበትን አንድ አላማ መቀየስ አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ግዴታም ጭምር ነው። ዛሬ በሁሉም አቅጣጫ ህዝቡ ታፍኖል ለነጌይቱ የሚያዘልቃቸውን የነፃነት ትንፋሽም ታግዷል ። ለዘመናት ኢትዮጵያ እንድትኖር ያበቁትን እነ አፄ ቴውድሮስ አፄ ምንሊክ እና ዘርዓይን እና ሌሎች ኢትዮጵያዊያን በከፈሉት መስዋትነት ሲሆን በሀገሬ ውስጥ ባርነትን አንቀበልም ብለውነውሞትንየተጋፈጡት።

ስለዚህ ነፃነት በልመና በነፃ እንደማይጎናፀፍ  በመሆኑ፣ ከሰማይ የሰላምና ነፃነት አምላክ  እሲኪወርድ ድረስ የምንጠብቅ ከሆነ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር ትኖራለች የሚል ግምት እንደማይኖር ነው።

በመቀጠል ደግሞ ለመላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ለማስተላለፍ የሚንፈልገው፧ ወያኔ የሕዝቡን ደም ደፍቶ በዝርፊያ ያካበታቸውን ሀብቶች ፣ የንግድና የኢኮኖሚ አውታሮች [ትራንስፖርትና መገናኛ ዘርፎች]በዘረፋ የተገኙ በመሆናቸሁ በነፃነትና በሰብአዊነት የሚያምኑ በውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በወያኔና በደጋፊያቸ የንግድና የኢኮኖሚ አውታሮች ላይ ማእቀብ እንድጫንባቸው።

በተለያዩ ሀገሮች በድብቅ ያካበቱ የንግድ ዘርፎች የዉጭ ምንዛሬ ምንጭ በመሆናቸውና በነዚ ሀብት በሚሰበሰበሁ በመጠቀም ሕዝቡን የሚጨፈጭፋበትን የጦር መሣሪያ በመሆኑ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ አቅሙን በሚፈቅደው ሁነታ ከነዚህ ዘርፎች ጋር አንዳችም የንግድ ግንኙነቶችን እንዳይኖር እንድቆጠቡ።

መንግስት መንግስትነትን የሚያሰኘው ማሟላት የሚገባቸዉ አላፊነቶችና ድርግቶች በጥቂጡ ለመግለጽ፣ በሕዝቡን መካከል ሰላም እንድሰፍን መጣር፣ በሕብረተሰቡ መካከል የሚፈጠሩ አለመግባቶች በሰላማዊ እንድፈቱና በማድረግ፣ የአንድነት ስመት እንድኖርና የአገርቷን ደህንነትና ድምበር ማስከበር ሲሆን ወያኔ ግን በተቃራኒ ሕዝቡን በዘርና በጎሳ እየከፋፈለ፣ እየገደለና የአገርቷን ንብረቶችን እየዘረፈ፣ መሬቱን ለውጭ አገር እየለገሰ፣ ለሰውነት ለነፃነትና ለዲሞኪራሲ እሉኝታ የሌለው፣በጎሰኝነት በዘረኝነት በብሕረተኝነት አጥብቀው የሚያምኑበት በመሆኑ ይህን ስርኀት መንግሥት ባለመሆኑ በሕዝቡ ደምና አጥንት የነደፋቸው ፀረ ሰው ሕገ ወጥ ሕጎች ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እንዳያከብራቸው ለጠቅላላው ሕዝብ ጥሪያችን እናስተላልፋለን።

በአንድነት በነፃነትና በእኩልነት በፍትህና በዲሞኪራሲ ላይ የተመሠረተ ስሪኀት እንድቋቋም የሚያስችል በጠቅላላዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትብብር ብቻ ነው። በዚሁ በመነሳት ዘረኛዉ የአረመኔ ስብስብ ሊፋለሙት የሚያችላቸውን አንድ ዓላማ በመነሳት፣ የፓለቲካ ድርጅቶች ልዩነቶች በማስወገድ፣ በአገር ስሜት ለአሁኑ አጣዳፊ የአገር ማዳን ጉዳይ በጋራ እንድንወጣ በአስቸኳይ ጥሪያችን ስናስተላልፍ፣ ለብዙ አመታት በተናጠል የተሞከሩ የነፃነት እንቅስቃሴዎች የትም እንዳላደረሱን የሚታሰብ ሲሆን አሁንም ከተለያዩ ድርጅቶች እና ብሄረስቦች መካከል የተጀመረውን የመተባበር መንፈስ በሰፊው እንዲቀጥል እና የጠቅላላው የኢትዮጵያ ህዝብ ምኞት በመሆኑ ድርጅታችን በዘር እና በክልል የተገደበ ባለመሆኑ ከጠቅላላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ተባብረን ለመስራት ዝግጁ መሆናችንን በዚህ አጋጣሚ ለመግለፅ እንወዳለን።

አንድ ኢትዮጵያ አንድ ህዝብ!

E‐mail: dec13codemo@gmail.com የታህሳስ ሶስት መታሰቢያ ዲሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ

The post “በአኮቦ ወረዳ ከ200 በላይ የሚሆኑ አኙዋኮች ህፃናት እና ሴቶች ተጨፍጭፈዋል” – ከታህሳስ ሶስት መታሰቢያ ዲሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ የተሰጠ መግለጫ appeared first on Zehabesha Amharic.

የአባይ ጸሃዬ ጦርነት በሚለው ላይ ምላሽ ለተስፋዬ ገብረአብ –ግርማ ካሳ

$
0
0

abay Tsehaye

ተስፋዬ ገበረአብ አንድ ወቅት የኢሕአዴግ ባለስልጣን የነበረ ሰው ነው። ጥሩ ጸሃፊ ነው። ከኦሮሞ ብሄረተኞች ጋር የቅርብ ግንኙነት አለው። አንድ ወቅት እንደዉም የኦሮሞ ተማሪዎች ማህበር ላይ የክብር እንግዳ ሆኖ ቀርቧል። በዚይ ወቅት “በሞጋሳ እኔም ኦሮሞ ነኝ” ነበር ይለው። ሞጋሳ አንድ ሰው “ኦሮሞ” ባይሆንም የኦሮሞን ባህልንና ቋንቋን ከተቀበለ፣ በኦሮሞ ሽምግሌዎች ፍቃድ “ኦሮሞ” የሚሆንብት ስርዓት ነው።፡(naturalized ኦሮሞነት)
ተስፋዬ “የአባይ ጸሐዬ ጦርነት” በሚል ርእስ አንድ ጽሁፍ አስነብቦናል። በጽሁፉ እነ አባይ ጸሃዬ አማራውን እና ኦሮሞውን በማጣላት በስልጣን ለመቆየት የማይፈነቅሉት ድንጋይ እንደሌለ ነው የገለጸው። ‘ከመነሻው በቋንቋ ላይ የተመሰረተ የፌደራል ስርአት ለመጠቀም ሲነሱ በህዝቦች መካከል በሚፈጠር አለመግባባት ስልጣናቸውን ለማቆየት እንደሚችሉ በማመን ነበር። በርግጥም ተጠቅመውበታል” ሲል ፣ በስልጣን ለመቆየት ሲባል ህዝብን በዘር ለመከፋፈል ከጠዋቱ ከጅምሩ የሕወሃት አጀንዳ እንደነበረ ነው የሚያስረዳን።

እዚህ ላይ ከተስፋዬ ገብረአብ ጋር በጣም እስማማለሁ። በተለይም አሁን ያለው በቋንቋ ላይ የተመሰረተው የፌዴራል ስርዓት ዋና አላማ፣ የብሄረሰቦችን መብት ለማስጠበቅ ታስቦ ሳይሆንን በሕዝብና በሕዝብ መካከል ግድግዳን በመፍጠር ከፋፍሎ ለመግዛት እንደሆን ብዙዎቻችን ደጋግምመን ስንጽፍፍበትና ስንናገረው የነበረ ጉዳይ ነው።

በነገራችን ላይ ተስፋዬ ራሱ የሕወሃት ባለስልጣን በነበረበት ጊዜ የዚህ በዘር የመከፋፈል እንቅስቃሴ አካል እንደነበረ መረሳት የለበትም። በተለይም የቡርቃ ዝምታ በሚል ርእስ የጻፈው፣ በፍጠራ ልአይ የተመረኮዘ መጽሐፍ ፣ ሆን ተብሎ በኦሮሞዎችን እን በሌላ ማህበረሰብ መካከል ትልቅ ጥላቻ እንዲኖር ያደረገ በጣም መርዛማ መጽህፍ ነበር።፡ታድዲያ አሁን ተስፋዬ፣ ከነርሱ ጋር ሲጣላ፣ ዞር ብሎ ስለ ወያኔ ዘረኘንት ሲነግረን ማየት ትንሽ ይያስቃል። ለምንኛውም፣ ግድ የለም ምናልብት የአመልክከት ለውጥ ተፈጥሮ ሊሆንን ስለሚችል የቡርቃ ዝማትን ለጊዜው ትቼ አሁን ወደጻፈው እመለሳለሁ።

ተስፋየ ለመግለጽ እንደሞከረው፣ ሕዝብን ክሕዝብ ለመለያየት ሆን ተብሎ ከመነሻው የተዘረጋው፣ በኦነግና በሕወሃት ተግባራዊ የሆነውን በቋንቋ ላይ የተመሰረተው የፌዴራል ስርዓት አንዱ ዉጤት “ኦሮሚያ” የምትባል ክልል መፈጥሯ ነው። ከዚይ በፊት ኦሮሚያ የሚባል ክፍለ ሃገር፣ ዞን፣ ወረዳ መንደር ኖሮ አያውቅም። ኦነግን የመንግስት አካል ለማድረግ ሲባል ብቻ የተፈጠረች ክልል ናት። ይች ክልል ፣ ለአስተድደር አመች ካለመሆኗ የተነሳ ለብዙ ግጭቶችና አለመስምማቶች ምክንያት ሆናለች።

ኦሮሚያን ጨመሮ አሁን ይሉት ዘረኛ የፌዴራል አወቃቀር የወለዳቸው ክልሎች፣ አሁን እንዳለው ቋንቋን ብቻ ሳይሆን፣ የአስተዳደር አመችነትን፣ የሕዝብ አሰፋፈርን፣ ባህልን፣ የህዝቡ ፍላጎትን፣ ኢኮኖሚን፣ ጂዮግርራፊን …ባካተተ መልኩ በጥናት፣ መስተካከል እንዳለባችው የብዙዎች እምነት ነው።

ተስፋዬ ገብረአብ ግን፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ለከፋፍለህ ግዛ ከመነሻው የተጠቀመብት የፌዴራል ስርዓት እንደሆነ ግሩም በሆነ ሁኔታ በሳፈረበት ብእሩ፣ ወረድ ብሎ ደግሞ “የአማራ ልሂቃን ቢያንስ ኦሮሚያን እንደ ክልል በማወቅ የመቀራረቡን መንገድ መክፈት ይጠበቅባቸዋል” ሲል በኦነግና በሕወሃት በሃይል በሕዝቡ ላይ የተጫነን ፌዴራሊዝም መቀበል እንደሚገባ ይነግረናል። በቀኝ እጅ የተገነባን በግራ እጅ ማፍረስ ይሉታል ይሄ ነው።
ሌሎች ብዙ ተስፋዬ ጫር ጫር ያደረጋቸው ነጥቦች አሉ። በተለይም “አማራ” ስለሚለው ማህበረሰ የጻፋቸው ትንሽ መስመር የለቀቁ አባባሎችን አንብቢያለሁ። ብዙም እዚያ ላይ አሁን ለጊዜው አላጠፋም። ግን ሳልጠቅስ የማላልፈው አንድ ነጥብ አለ።

በኦሮሚያ የተነሳውን ተቃዉሞ በመደገፍ፣ በኦሮሚያ ባሉ ትላልቅ ከተሞችና በሌሎች ክልሎች ያለው ማህበረሰብ ተነስቷል ማለት አይቻልም። ይሄም የራሱ የሆነ ምክንያቶች አሉት። ዶር መሳይ ከበደ እንደጻፊት ላለፉት 25 በነበረው ሁኔታ ጥርጣሬ መኖሩ (ብዙዎች በኦሮሞ አክራሪዎች ጥቃት ሲፈጸምባቸው፣ ከቅያቸው ሲባረሩ ስለነበረ …) አንድ ምክንያት ነው። ሕዝቡ አለመደራጀቱ፣ የኦሮሞ ተቃውዋሚዎች ይዘዉት የነበረው አጀንዳ አገር አቀፍ አለመሆኑ እንደ ሌሎች አበይት ምክንያቶች ሊጠቀሱ ይችላሉ። ሆኖም ተስፋዬ ገብረዓብ፣ ምክንያቶችን ከመረዳት ይልክ፣ የኦሮሞዎችን ተቃዉሞ አልደገፉም በሚል፣ ለሌላው ማህበረሰብ ማስጠንቀቂያ ቢጤም ለመስጠት የሞከረበት ሁኔታ ነው ያለው።

“በቅርቡ የወያኔ ነባር አባል ከሆነ የቀድሞ ወዳጄ ጋር በፅሁፍ ስናወጋ” ያለው ተስፋዬ፣ ይሄ ወዳጁ “የሞጋሳ ዘመዶችህ(ኦሮሞዎች ማለቱ ነው) አይሳካላቸውም። አማሮች ለታክቲክም ቢሆን ከኛ ጋር ናቸው።” እንዳለው ጽፏል። ሌላም ማህበረሰብ ከወያኔዎች ጎን እንደቆመ ነው ሊያመላክተን የሞከረው። አንድ ማህበረሰብ ዝም አለ ማለት አገዛዙን ደገፈወደ ማለት ድምዳሜ እንደመድረስ ነው። በአዲስ አበባ ከ200 በላይ ዜጎች ሲረገፉ ሌሎች አልተነሱም ነበር። በባህር ድዳር

ወረድ ብሎም “ የኦሮሞ ህዝብ አመፁን አጠናክሮ ቀጥሎ ብቻውን የወያኔን ስርአት ለማስወገድ ከበቃ ለሌላው ወገን ለፀፀት የሚያበቃ ታሪካዊ ስህተት ይሆንበታል። በአብሮ መኖር ሂደት ሌሎች የሚሉትን መስማት ቀዳሚ ጉዳይ ነው። የኦሮሚያን አመፅ ሌሎች ኢትዮጵያውያንም እንዲሳተፉበት ሲጠየቁ፤ ለነገ አብሮነት በማሰብ እንጂ የኦሮሞ ህዝብ ብቻውን ወያኔን ማንበርከክ አይችልም ከሚል አልነበረም። ይህን አብሮ የመታገል ጥያቄ በተሳሳተ መንገድ የተገነዘቡ ወገኖች ወያኔን ስልጣን ላይ በማቆየቱ ረገድ የማይናቅ ድርሻ እያበረከቱ ነው” ሲል ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የኦሮሞዎችን ንቅናቄ ሌላው መደገፍ እንዳለበት ያስጠነቅቃል።

ይህ አይነትት አቀራረብ በጣም አደገኛ አቀራርብ። የኦሮሞ ብሄረተኞች ተስፋዬ እንዳለው የኦሮሚያ ትላልቅ ከተሞች ሳያቅፉ ፣ ሌላውን ማህበረሠብብ አግለው ለብቻው የሚያመጡት ዉጤት ይኖራል ብዬ አላስብም። ላለፉት ሁለት ወራት የተደረጉት እንቅሥቃሴዎች ለውጥ ካላመጡ ምንም አይነት እቅንስቃሴ ነው ለዉጥ የሚያመጣው ? መቼም የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን እንዲሰረዝ ተደርጓል የሚል መልስ አይይቀርብም። ማስተር ፕላኑ በሌላ መልኩ መተግበርኡ አይቀሬ ነው።

ይህ የተጀመረውና በጣም ምመቅዛቀዝ እየታየበት የመጣው የኦሮሞዎችን እንቅስቃሴ በቶሎ ሌሎችን ባቀፈ መልኩ እንዲሰፋ ካልተደረገ ፣ በዚህ ረገድ የኦሮሞ ልሂቃን ምመሰረታዊ የሆነ የአካህእድ ለውጦችን ካላደረጉ፣ በጣም ትልቅ ታሪካዊ ስህተት ነው የሚሠራው። ሌሎችን ማስጠንቀቅና በልእሎ ላይ መዛት ሳይሆን፣ የሌሎች ጥያቄ ምንድን ነው ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል። ሌልአው ማህበረሰብ እኮ ላለፉት 25 አመታት በኦሮሚያ ዉስጥ ሲፈናቀል፣ ሲገደል፣ ኦሮሞ አይደለህም ትብሎ ከሥራ ሲባረር ..የነበረ ነው። ብዙ ግፍ የተፈጸመበት ነው። ይህ ማሀብረሰብብ ቢፈራና ቢጠራጠር በጭራሽ ሊወቀስ አይገባውም።

የኦሮሞ ልሂቃን “ኦሮሚያ፣ ኦሮሚያ..” የሚሉትን አቁመው፣ ጥያቄው የምብት፣ የፍትህ ጥያቄ ነው በሚል ለምን በኢትዮጵያ የዜጎችን ጣይቀእ ህኡሉ የምኢያከበር ዴሞክራሲያዊ ስር፤ዓት እንዲገነባ አይነሱም? የኦሮሞ መሬት የወሰደ ከሚሉ መሬቱ የሌሎቻ ያለሆነ ይመስል፣ ለምን ገበሬው የመሬት ባለቤት ይሁን አይይሉም ? የዲሞክራሲ ስርዓት ከተገነባ ፣ ሕዝቡ ከፈለገ በአጼ ጊዜ የነበረው አወቃቀር፣ ከፈለገ ዓሁን ያለውን፣ ከፈለገ ደግሞ ሌላ አዲስ ….ማዋቀር እንደሚችል ለምን ስምምነት ማድረግ ይሳናቸዋል ? ለምን ኦሮሚያ ወይንም ሞት የሚል አቋም ይይዛሉ ? ኦሮሚያ መኖር አለበት ካሉ በኦሮሚያ ዉስጥ መሆን የማይፈለገውስ ማህበረሰብ ? 75% የሚሆነው የአዳማ ህዝብ፣ 990% የሚሆነ የአዲስ አበባ ህዝብ፣ 60% የሚሆነው የጂማ ህዝብ፣ ከ80% በላይ ይየሚሆኑት የቢሾፍቱና የሻሸመኔ ነዋሪዎች ….

ይልቅ የሚያዋጣው ግትርነትት ሳይሆን ነገሮች በርጋታ ተመልክቶ፣ የሁሉንም መሰረታዊ ጥያቄ በመለሰ መልኩ መግባባቶች እንዲኖሩ ማድረግ ነው። ለዚኅም በዋናነት ቁልፍ ሥራ መስራት ያለባቸው የኦሮሞ ልሂቃን ናቸው።፡ሌላአ ማህበረሰብ በኦሮሞ ክራሪዎች ላለፉት 25 ሲገፋ የነበረ ነው። ይሄንን ሕዝብ ማቀፍ የግድ ያስፈልጋል። ሌላው ይቅር በኦሮሚያ ያሉትን ትላልቅ ከተሞች ማቀፍ ያስፈለጋል።፡በኦሮሚያ ያሉ ትላልቅ ከተሞች ደግሞ multi-ethnic ናቸው።

The post የአባይ ጸሃዬ ጦርነት በሚለው ላይ ምላሽ ለተስፋዬ ገብረአብ – ግርማ ካሳ appeared first on Zehabesha Amharic.

በጋምቤላ በኑዌር እና በአኝዋኮች መካከል በተፈጠረ ግጭት 6 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰማ

$
0
0

Zehabesha News

(ዘ-ሐበሻ) በጋምቤላ ከተማ በኑዌሮች እና በአኝዋኮች መካከል በተነሳ ደም ያፋሰሰ ግጭት የ6 ሕይወት ማለፉን የዘ-ሐበሻ የዜና ምንጮች ከስፍራው ዘገቡ::

ባለፈው ሳምንት አንድ ሰው መሞቱን ተከትሎ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ በተከሰተው ግጭት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች እንደቆሰሉ ምንጮቻችን ዘግበዋል::

በሁለቱ ብሔረሰብ ግጭቶች በስተጀርባ የሕወሓት እጅ እንዳለበት የሚጠቅሱ የፖለቲካ አክቲቭስቶች በተለይ የአኝዋክ አክቲቭስቶች ከኑዌር ማህበረሰብ በስተጀርባ ሕወሓት እንዳለበትና ጠመንጃ እንዳስታጠቃቸው ይከሳሉ::

ተጨማሪ መረጃዎችን ዘ-ሐበሻ ይዛ ትመለሳለች::

The post በጋምቤላ በኑዌር እና በአኝዋኮች መካከል በተፈጠረ ግጭት 6 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰማ appeared first on Zehabesha Amharic.

አቡነ ማትያስ መህበረ ቅዱሳንን አፈርሰዋለው ሲሉ የማፍረሻውን ትዕዛዝ ማን ሰጣቸው? ቅዱስ ሲኖዶስ? ወይንስ….? ። –ከተማ ዋቅጅራ

$
0
0

H_E_Abune_Matiyas_Archbishop_of_Jerusalem_Misaያልፈረሰን ማፍረስ ያልተነቃነቀን ማነቀነቅ በአንድነት ለዘመናት ተዋደው እና ተፋቅረው የኖሩትን ህዝብ መበተን የኢትዮጵያኖች የእለት ተእለት ዜና ከሆነ ስንብቷል። ዛሬም በአንድነት እና በጥንካሬአቸው  ለቤተ ክርስትያን እውቀታቸውን፣ ገንዘባቸውን፣ ጉልበታቸውን ሳይሳሱ በመስጠት የቤተክርስትያን ልጅነታቸውን በማስመስከር ያልተማረን እንዲማሩ በማርደግ፣  የአብነት ትምህርት ቤቶችን ህንጻዎችን በማነጽ እንዲጠናከር በማድረግ፣ ቤተክርስትያንን  በቅንነት በማገልገል ወጣትነት ሳያታልላቸው በጉብዝናህ ግዜ እግዚአብሔርን አስብ የሚለውን አምላካዊ ቃል እየፈጸሙ ያሉትን ወጣቶች የበለጠ ፍቅር፣ የበለጠ አባታዊ ምክር፣ የበለጠ ቤተ ክርስትያኗ ድጋፍ፤ ማድረግ ሲገባቸው የቤተክርስትያኗ መሪ በተባሉት በአቡነ ማቲያስ የሰላ ትችት እየተሰጣቸው እጅና እግራቸውን አስሬ ካላስቀመጥኳቸው ተብሎ ዛቻዎችን ስንሰማ እንደ ቤተክርስትያን ልጅነታችን የሚያም ጉዳይ ነው። ማን አይዞት ብሎዎት ነው የቤተክርስትያን ልጆችን ለማሰር የተነሱት? የየትኛውስ አካል ለማስፈጸም ነው ማህበረ ቅዱሳንን ለማፍረስ የተነሱት?

የማህበረ ቅዱሳን አባል ከአለማዊ ትምህርት የአለማዊ ትምህርታቸውን ጠንቅቀው የተማሩ ከመንፈሳዊ ትምህርታቸውም መንፈሳዊ ትምህርታቸውን በደንብ የተማሩ የተማሩትንም በስራ ላይ የሚያውሉ በአባቶች መሰረት ላይ የተመሰረቱ የቤተክርስትያን አገልጋዮች ናቸው። ማህበረ ቅዱሳን በቁጥር በጣም ብዙ የሚባል አባል እንዳለው የሚታወቅ ሲሆን አገልግሎታቸውም እንደ ቁጥራቸው በጣም ሰፊ ነው። በመላው ኢትዮጵያ የሲኖዶስ አባቶች ሊደርሱበት ያልቻሉትን ቦታዎች ጭምር በመድረስ የቤተክርስትያን ልጅነታቸውን በማስመስከር የተዘጉ ቤተክርስትያንን በማስከፈት፣ ሊዘጉ ያሉትን ሳይዘጉ በመድረስ በተጠናከረ ሁኔታ ቀጣይነት ባለው መልኩ አገልግሎት እንዲቀጥል በማድረግ ቋሚ መገልገያ በመትከል እራሳቸውን በራሳቸው የሚያስተዳድሩበትን ስራ በመስራት ከፍተኛ ተጋድሎ  እያደረጉ ያሉ የቤተክርስትያን ልጆች ናቸው።

የማህበረ ቅዱሳን እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ብቻ የተወሰነ  ሳይሆን በመላው አለም የተዘረጋ በግዜ እና በቦታ ሳይወሰኑ ለቤተክርስትያን ቅድሚያ በመድረስ አገልግሎት በመስጠት ያለ ስብስብ ነው። ቅዱሳኖች ግዜአቸውን፣ እውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውን ለቤተክርስቲያን በመስጠት ከእግዚአብሔር የአገልግሎታቸውን ዋጋ የጽድቅ አክሊል ተቀብለዋል። የስሙ ስያሜውም እንደሚነግረን የማህበረ ቅዱሳን አገልግሎት ከዚህ የተለየ ባለመሆኑ ማህበረ ቅዱሳን ተብሏል። የቅዱሳንን ፈለግ ተከትለዋልና።

ታዲያ አቡነ ማቲያስ ማህበረ ቅዱሳንን ማፍረስ ለምን አስፈለጋቸው? እውነተኛ አባት ቢሆኑ ልጆቻቸው  በቤተ ክርስትያን ተሰብስበው ሲያዮ ደስ ሊላቸው ሲገባ… ልጆቻቸው  ተሰብስበው ስለቤተክርስትያን በአንድነት ሲቆሙ ሊያኮራቸው ሲገባ… ልጆቻቸው ገንዘባቸውን፣ እውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ሳይሳሱ ለቤተክርስትያን ሲሰጡ ሊኮሩባቸው እና የበለጠ እንዲተጉ ሊያበረቷቷቸው ሲገባ አስሬአቸው እነሱን ሳላጠፋ እንቅልፍ አይወስደኝም ተብሎ መዛቱ ከፓትሪያሪክ የሚጠበቅ ነውን? ሲኖዶሱ ልጆቻቸው እጅና እግራቸው ታስሮ ከቤተክርስትያን መጥፋት አለባቸው ተብለው ሲዛትባቸው የማህበሩ አባላት ካልጠፉ እንቅልፍ እንደማይተኝ ሲነገርባቸው ምን ተሰምቷችሁ ይሆን?

ሲኖዶስ ከዚህ በፍት አቡነ ማትያስ ላይ በማህበረ ቅዱሳን እና በሌላ ቤተክርስትያናዊ ጉዳዮች ላይ አቡኑ በግላቸው ጥቂት ግለሰቦችን ሰብስበው ከሳቸው ጋር እንዲቆሙ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ላይ ጠንካራ አቋም በማሳየት የአቡኑን ሃሳብ በሙሉ ውድቅ በማድረግ ጥንካሬአቸውን አይተናል። እኛም በእውነተኛ አባቶች በሲኖዶሱ ውሳኔ እጅጉን ኮርተናል። ዛሬ ለምን ተመልሶ መጣ? ተመልሶ ሲመጣስ የሲኖዶስ ውሳኔ ምን ይሆን? ወደፊትስ ተመልሶ እንዳይመጣ ምን አይነት ውሳኔ ይሆን የሚወሰነው?

እንደ ቀልድ በሚሊዮን የሚቆጠር ስብስብን እግሩን እና እጁን አስረዋለው ብሎ  መናገር ከቤተክርስትያን አባት ይጠበቃልን? የአባቶች ድርሻ እኮ ያልተሰባሰቡትን ወደ ቤተክርስትያን መሰብሰብ እንጂ በቤተ ክርስትያን ስር የተሰበሰቡትን ከቤተክርስትያን ማባረር አይደለም። በእግዚአብሔር ቤት ላይ ሹመት የተቀበላችሁት በቤተክርስትያን ጥላ ስር የተሰበሰቡትን ለማፍረስ እና ለመበታተን ነው እንዴ? በእውነተኛዋ ቤተክርስትያን ስር በፍቅር ተሰብስበው በጥላዋ ያረፉትን እንደ ሰው ፍላጎት በቀላሉ ማፍረስስ ይቻል ይሆንን? በቤተክርስትያን  ስር ያለመለያየት በአንድነት የተሰበሰቡትን የቤተክርስትያን ልጆችን አፈርሳችኋለው ብሎ መናገር የቤተክርስትያን አባቶች ሃሳብ ወይንስ የሌላ አካል ሃሳብ?

አቡነ ማቲያስ መሐበረ ቅዱሳንን አፈርሰዋለው ብለው ይናገሩት እንጂ ከኋላቸው  ማን እንዳለ የታወቀ  ነው። ማህበረ ቅዱሳን ያሰባሰባቸው ሁሉም የቤተክርስትያን ልጆች መሆናቸው ብቻ ነው። የማህበሩ አባል የሚሆነው ወይንም የሆኑት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ  አማኝ የሆነ ብቻ ነው። ምንም አይነት የፖለቲካ አላማ  የሌለው ማህበር ነው። የዘር የቀለም ልዩነት የለም።በእርግጠኛነት ለመናገር ከሁሉም ብሄሮች ውስጥ የተዋህዶ ልጅ ከሆነ የማህበሩ አባል መሆን የፈለገ መሆን ይችላል። ወደዚህ ማህበር ሲመጣ ስለ ብሔር ወይንም ስላለህ ፖለቲካ አመለካከት ቦታ የለውም። ምክንያቱም የማህበሩ ምስረታ ምድራዊ መንግስትን ለማገልገል ሳይሆን ሰማያዊ መንግስትን መስበክ ስለሆነ። ምድራዊ ስልጣንን ለማስገኘት ሳይሆን የማታልፈውን የእግዚአብሔር መንግስት ለማውረስ ስለሆነ። ስለዚህ የሐጥያት ስር የሚባሉት ዘረኝነት፣ ወገኝተኝነት፣ገንዘብ ወዳድነት፣መለያየት የመሳሰሉት በማህበሩ ውስጥ ቦታ የሚሰጣቸው ጉዳዮች አይደሉም። ስለዚህ እውነተኛ ኢትዮጵያዊነት እና የእግዚአብሔር አገልጋዮች የሚገኙበት ማህበር ነው። ከየትም ይምጣ ከየት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጅ ከሆነ የዚህ ማህበር አባል መሆን ይችላል። ማህበሩን የማታውቁት አለ ብዬ መናገር ባልደፍርም ካላችሁ ግን ያለው እውነት ይሄ ነው።

ማህበረ ቅዱሳንን ማፍረስ የተፈለገበት ዋናው አላም ለመንግስት ፖሊሲ የተመቸ ስላልሆነ ነው። እንደ መንግስት ሃሳብ በዘር የተደራጀ ቢሆን ኖሮ አልያም የመንግስት ደጋፊ ሆነው መንግስት የሚፈልገውን የማለያየት ስራ የሚሰሩ ቢሆኑ ኖሮ ወይንም እንደ መንግስት ሃሳብ ኢትዮጵያን የማፍረስና  ታሪኳን የማጥፋት ስራ የሚሰሩ ቢሆኑ ኖሮ የኦርቶዶክስ አማኝ በሙሉ ወደዚህ ማህበር እንዲገቡ መንግስት ያስገድድ ነበረ። ይሄ ባለመሆኑ ዘረኝነት የእግዚአብሔርን መንግስት አይወርስም ታሪካችንንም ለአፍሪካ ብሎም ለአለም ህዝብ ምሳሌ ነው በማለት አንድነት፣ ፍቅር፣ የእግዚአብሔር መንግስት የሚሰበክበት ማህበር በመሆኑ ዘረኝነት ነብሳቸው ትጸየፋዋለች ጥላቻንም አያስተምሩም ፍቅር ቤታችው፣ ፍቅር አገራችው፣ ፍቅር አምላካችው ነው በመሆኑ መንግስት ለማፍረስ ተነሳ። እንደተለመደው መንግስት እጄ የለበትም ለማስባል ሁሉንም በራሳቸው ሰዎች ከኋላ ሙሉ ድጋፍ በመስጠት  የሚያስመታው። ነገሮች አቅጣጫውን ስተው ጠንካራ ተቃውሞ ገጥሞት መቀልበሻው ሲጠፋውና ሲጨንቀው ደግሞ እርቅ ይላል። አቡነ ማቲያስ በማህበረ ቅዱሳን ላይ የመነሳታቸው ሚስጢር 100% የመንግስት መዶሻ ሆነው ማህበሩን ለመምታት የተነሱ አባት ናቸው እንጂ ለቤተክርስትያን በመቆርቆር ከቤተክርስትያን አባቶች ጋር ተማክረው  የቤተክርስትያንን መሰረቷን ለማጥበቅ የተነሱ እንዳልሆነ ጥንቅቀን እናውቃለን።

የቤተክርስትያንን ህልውና የሚፈታተንና ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነገር ከፊታችን ቀርቧል እኛ ልጆቿ ከእግዚአብሔር ዋጋ የምናገኝበት አልያም የምናጣበት።

ይሄንን ሁላ የምለው የማህበረ ቅዱሳን አባል ሆኜ አይደለም ነገር ግን እንደ ቤተክርስትያን ልጅኔቴ የቤተክርስትያን ጉዳይ ስለሚያገባኝ ነው። ስለ ቤተክርስትያን ጉዳይ ዝም ማለት አየር ሳትተነፍስ መኖር አንድ ነው። ስጋዊ ህይወትህ ማኖር ካለብህ ለደቂቃም ማጣት የማትችለው ነገር አየር ነው። ነፍስህን ለዘላለም በእግዚአብሔር እቅፍ ማኖር የምትችለው ቤተክርስትያን ስትኖር ብቻ ነው። ስለዚህ ስለ ቤተክርስትያን ዝም አንልም።

ከተማ ዋቅጅራ

28.01.2016

Email- waqjirak@yahoo.com

 

The post አቡነ ማትያስ መህበረ ቅዱሳንን አፈርሰዋለው ሲሉ የማፍረሻውን ትዕዛዝ ማን ሰጣቸው? ቅዱስ ሲኖዶስ? ወይንስ….? ። – ከተማ ዋቅጅራ appeared first on Zehabesha Amharic.

የኦሮሞን ሕዝብ ትግል ከመጠራጠር  ይልቅ ለሱዳን የሚሰጠውን መሬት ለማስቆም ሌላው ሕዝብ አሁን ይነሳ

$
0
0

ethiopia sudan Boarder

በኦሮሚያ የተነሳው ሕዝባዊ አመፅ አሁንም ተቀጣጥሎ በቀጠለበት በአሁኑ ሰአት በሌላው የኢትዮዽያ ክፍል ግን አልፎ አልፎ ጎንደር ላይ ከሚሰማው ውጥረት በስተቀር ይህ ነው የሚባል ምንም አይነት የአመፅ እንቅስቃሴ አይታይም። በተለያዩ ሚዲያዎች ወይም ድሕረ ገጾች ሌሎች ክልሎች ሕዝባዊ አመፁን እንደሚቀላቀሉና በኦሮሞ ህዝብ ያለዉ ጥያቄ በሌሎች ክልሎችም እንዳለና አንድ ቀን ሊፈነዳ እንደሚችል ሲነገር ቆይቷል ነገር ግን እስካሁን አመርቂ የሆነ እንቅስቃሴ በሌሎች ክልሎች የተደረገበት ሁኔታ የለም። አንዳንድ ከኦሮሚያ ክልል ውጪ ያሉ ፖለቲከኞች እንደሚሉት ከሆነ ሌላው ክልል አመፁን ያልተቀላቀሉበት ምክንያት በትግሉ ላይ ጥርጣሬ ስላላቸው ፣ ወይም አንድ ፀሀፊ እንዳስቀመጡት በኦሮሚያ እና በአካባቢዋ የተነሳውን ሕዝባዊ አመጽ ሌሎች ክልሎች ያልተቀላቀለበት ምክንያት በኦሮሞ ሕዝባዊ አመጽ ውስጥ የማያምኑት ንጥረ ብሔርተኝነት አለ ወይም ይኖራል ብለው በመፍራታቸው ነው። ስለዚህ ትግሉ Oromo Protest የሚለው Ethiopian Protest በሚለዉ መቀየር ይኖርበታል ይላሉ። ሌላው ደሞ በተለይ ስለ ርዕሰ መዲናዋ ፊንፊኔ ወይም አዲስ አበባ ሲነሳ አምስት ለአንድን መደራጀት እንደትልቅ ምክንያት ይጠቀሳል ነገር ግን ሁለቱም ምክንያት ውሃ የማይቁዋጥሩ ናቸው።

 

አምስት ለአንድ ከሚለው ከሁለተኛው ምክንያት ልነሳ። አምስት ለአንድ የሚባለው የስለላ መረባቸውን ፋሺስት TPLF በመላው ኢትዮዽያ ሲጠቀሙበት ቆይተዋል። ነገር ግን እንኩዋን የተማረው ያልተማረው ጀግናው የኦሮሞ ገበሬ አፈራርሶ ከጥቅም ውጪ አድርጎታል። ጉዳዩ ምንም የተለየ ሚስጥር የለወም ይህ ከታች ያለውን ምስል እንመልከት። ይች የምታዩዋት ፈረስ በመጀመሪያ ሰሞን ጠንካራና የማይነቃነቅ ግንድ ላይ ነበር ስትታሰር የቆየችው አሁን ግን አንድ ፕላስቲክ ወንበር ላይ ታስራ ሳትንቅሳቅስ እንደ ድሮው ጠንካራና የማይነቃነቀው ግንድ ላይ የታሰረች መስሏት ቆማለች። ይህ የሚያመለክተው የዚህች ፈረስ የታሰረው አእምሮዋ እንጂ አካሏ አይደለም። ስለዚህም የአዲስ አበባ ህዝብ ያልተነሳው የአምስት ለአንዱ አደረጃጀት ጥንካሬ ሳይሆን በውስጡ ባለው አላስፈላጊ የሆነ ጥርጣሬ እና ፍራቻ ነዉ። አምስት ለአንዱን እናፍርስ ከተባለ የሚያስፈልገው ቆራጥነትና ዋጋ መክፈል ብቻ ነው። የኦሮሞ ሕዝብ ወያኔዎች ልጆቹን በገደሉበት ወቅት ቀብሮ ዝም ብሎ ወደቤቱ አልተመለሰም ይልቁንም ሞት አያቆመንም በማለት የቀብሩን ስነስረዓት እየቀየረ የተቁዋሞ መድረክ እያደረገው አመጹን ቀጥልዋል። ለውጥ ለማምጣት መስዋት መሆን የግድ ነው ብሎም ያምንል።

 

አሁን ደግሞ ትግሉ ብሔርተኝነት በውስጡ አለ በሚል ሌሎች ብሔሮች በጥርጣሬ ያዩታል ስለዚህ ትግሉ Oromo Protest የሚለው Ethiopian Protest ወደሚለው መቀየር ይኖርበታል ወደሚለው ልመለስ። በመጀመሪያ ደረጃ የ25 አመቱ ግፍና መከራ አንገሽግሾት አመጹን ያለምንም ማመንታት ውድ ልጆቹን መሰዋእት በማድረግ ከሁለት ወራቶች በላይ እያካሄደ ያለው የኦሮሞ ሕዝብ ነው። ስለዚህ Oromo Protest የሚለው የአመፁ መጠሪያ ብዙም የሚያከራክር አይደለም። ሲቅጥል 45 ምሊዮን ከሚሆን ህዝብ አንድ አይነት አመለካከት ብቻ መጠበቅ የለየለት ሞኝነት ይመስለኛል። ስለዚህ የኦሮሞ ሕዝብ እየሞተ ትግሉን በቀጠለበት ወቅት ሌላው ህዝብ የችግሩ ተጠቂ ሆኖ ዝምታን ሲመርጥ ብሄርተኝነት በተቁዋሞ ውስጥ መንፀባረቁ የሚገርም አይሆንም።

 

ትግሉን ከOromo Protest ወደ Ethiopian Protest መቀየር ከተፈለገ የቀረዉ ሕዝብ እንደ ኦሮሞ ሕዝብ መነሳት በቂ ይናሆል። እዚህ ጋር ሌላው ሕዝብ ለመነሳት የኦሮሞ ሕዝብ ትግል አጋር መሆን ወይም መቀላቀል ሳይሆን የሚያስፈልገው የራሳቸውን ችግር ማንሳት ብቻ በራሱ ከበቂ በላይ ነው። የትኛውም ክልል ወይም ብሔረሰብ በወያኔ መራሹ የወንበዴ ጥርቅሞች ላይ ለመነሳት እልፍ አእላፍ የሆኑ ከበቂ በላይ ምክያቶች አሉት። እስቲ ለአብነት ያህል ልክ እንደ ኦሮሚያው ለህዝባዊ እምቢተኝነት የሚያበቁ ምክንያቶችን በስፋት ሕዝባዊ ተቃውሞ ይነሳባቸዋል ተብሎ የሚጠበቁ የተወሰኑ ክልሎች ወስደን እንመልከት። በመጀመሪያ አማራ ክልል ቀጥሎ ደሞ ርዕሠ መዲናዋን ከዚያ ጋምቤላ ወስደን እንመለከታለን።አሁንም ወያኔዎች የሚያደርሱት ልክ የሌለው የ25 አመቱ ግፍና በደል እንዳለ ሆኖ ልክ ከኦሮሚያ ክልል ተነጥቆ ለአዲስ አበባ ሊሰጥ እንደነበረው ወልቃይት በሀይል ወደ ትግራይ አልተካለለም፧ ዋልድባ ገዳም በግፍ ለኢንቨስተሮች አልተሸጠም፧ ከሁሉ የሚብሰው ደሞ ከጎንደር ሰፊ መሬት ተነጥቆ ለባዕድ ሀገር ሱዳን ለመስጠት ወያኔ የካርታ የማንሳት ስራዋን እያጠናቀቀች አይደለምን፧ ካሉት አያሌ ምክንያቶች ለህዝባዊ እንቢተኝነት እነኝህ ከላይ የተጠቀሱት ከበቂ በላይ ናቸው።

 

አዲስ አበባ ከምርጫ 97 ጋር በተያያዘ በአንድ ቀን ከ 200 የሚበልጡ ዜጎችዋን አጥታ ደም ዕንባ አላነባችም፧ ነጋዴ በግፍ ከገበያ ሲስተም እንዲወጣ አልተደረገም፧ በአረብ ሀገር ግፍና በደል ለደረሰባቸው ወገኖች ሰልፍ የወጡ ዜጎች በአጋዚ ወታደሮች አልተቀጠቀጡም፧ በሊብያ በአሸባሪዎች ለተቀሉት ወገኖች መንግስት እራሱ በጠራው ሰልፍ ላይ የተገኙ ዜጎች በአደባባይ የዱላ ውርጅብኝ አልወረደባቸውም፧ የጋምቤላ ህዝብ ከመሬቱ በኢንቨስትመንት ስም አልተፈናቀለምን፧ የጋምቤላ ክልል ከ400 በላይ ዜጎቹን አጥቶ የፍርድ ያለህ አያለ እየጮኸ አይደለምን፧ ኡጋዴን ሲዳማ እያልን ብንቀጥል ለሕዝባዊ አመፅ የሚያበቁ በርካታ ምክንያቶች አሉ።

 

ታዲያ ይሄ ሁሉ መከራና ስቃይ እየደረሰበት ሌላው ብሔረሰብ ያለመነሳቱ ሚስጥር ምን ይሆን፧፧፧ ልክ ፀሀፊው እንዳስቀመጡት በኦሮሚያ እና በአካባቢዋ የተነሳውን ሕዝባዊ አመጽ የሌላ ብሄረሰብ ሰዎች ( በይበልጥም አማራው ) ያልተቀላቀለበት ምክንያት በዚህ በኦሮሞ ሕዝባዊ አመጽ ውስጥ የማያምኑት ንጥረ ብሔርተኝነት አለ ወይም ይኖራል ብለው በመፍራታቸው ከሆነ ገና ለገና የኦሮሞ ብሔርተኝነትን በመፍራት አማራው ለመብቱ መከበር ላይነሳ ነው፧ ወልቃይትንም አሳልፎ ሊሰጥ ነው፧ ሁሉም ይቅር የጎንደር መሬት ተቆርሶ ለሱዳን ሲሰጥ ዝም ብሎ ሊመለከት ነው፧ እምቢተኝነቱ በጥርጣሬ ታየ አልታየ የኦሮሞ ሕዝብ ከመቼውም በላይ ጥንካሬውን እያሳየ ተቃዉሞውን ሳያቁዋርጥ ወደፊት እየገፋ ነው። ዋናው ነገር እዚጋ የኦሮሞ ህዝብ እምቢተኝነት ፣ ብሔርተኝነት ይኑረው አይኑረው የሚወሰነው በሕዝቡ ነው። ስለዚህ የኦሮሞ ሕዝብ እንቢተኝነት በውስጡ ብሔርተኝነት አለበት ከማለት ይልቅ ሱዳን ድንበራን አካላ ሕጋዊ ከማድረጉዋ በፊት ወያኔ የማካለሉን ስራ ተግባራዊ እንዳታደርግ የአማራው ሕዝብ ሌላውን በማስተባበር ሕዝባዊ እምቢተኝነቱን ከዳር እስከዳር አንቀሳቅሶ ልክ እንደ ማስተር ፕላኑ ተግባራዊ እንዳይሆን ማስቆም አለበት።

 

አድ አዳማ(Norway)

The post የኦሮሞን ሕዝብ ትግል ከመጠራጠር  ይልቅ ለሱዳን የሚሰጠውን መሬት ለማስቆም ሌላው ሕዝብ አሁን ይነሳ appeared first on Zehabesha Amharic.


ወልቃይት ጠገዴ ማነው?

$
0
0

welkayet - satenaw

መግቢያ

ወልቃይት ጠገዴ ማነው? የሚለው “ሊበሏት ያሰቧትን ….” አይነት ጥያቄ በተደጋጋሚ የሚነሳው ከማን በኩል እንደሆነ ማወቅ “ሊበላን” ያሰፈሰፈውን አስቀድሞ ለማወቅ ይረዳል የሚል እምነት አለን። ከዚህም በመነሳት ባደረግነው ጥናትና ክትትል ጥያቄው ተደጋግሞ የሚነሳው በትግራይ ነጻ አውጭ ቡድን በኩል ሲሆን ይህ ወራሪና ተስፋፊ ቡድን ለመጀመሪያ ጊዜ የወልቃይትን መሬት በረገጠ ወቅት በአቶ ስብሃት ነጋ አዛዥነትና በአቶ መኮንን ዘለለው አጥኝነት ጥያቄው ለወገናችን ቀርቦ ነበር። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ለዚህ እኩይ ቡድን በተንበረከኩና ባደሩ፤ ይልቁንም የዚህን ወንጀለኛ ቡድን በህዝባችን ላይ የፈጸመውን የዘር የማጽዳት ወንጀልና በሃይል ወደ ትግራይ የከለላቸውን የጎንደር ታሪካዊ ለም መሬቶች ህጋዊ ሽፋን ለመስጠት በሚዋትቱ ጥቂት ተንበርካኪዎች በኩል ጥያቄው ዳግም ሲነሳ እየሰማን ነው። 

በተለይም በቅርቡ አቶ ሃይሉ የሺወንድም የተባሉ የአካባቢው ተወላጅ በጃንዋሪ 6, 2016 “የወልቃይት ባህልና የማንነት ጥያቄ” በሚል በኢትዮሚዲያ ድረ-ገጽ ላይ ባሰራጩት ባለ 8 ገፅ ፅሁፍ ላይ ለአለፉት 37 ዓመታት ህወሃትን በወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን የዘር ማፅዳትና በትግሪያዊነት የመተካት ወንጀል ለመግታት በታገሉና ለኢትዮጵያና ለመላው የዓለም  ህዝብ ባጋለጡ በስደት በሚገኙ የአካባቢው ተወላጆችና በሃገር ውስጥ ሆነው “የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት”ን ለማስከበር ለሚታገሉ ወገኖች ይህን የማንነት ጥያቄ ደጋግመው ሲጠይቁና እርስ በእርሳቸው የሚቃረኑ ሃሳቦችን በማንሳት አንባቢውን ግራ ለማጋባት ላይና ታች ሲዋትቱ ተመልክተናል።

ስለሆንም ይህን በጥቂት እውነትነት ያላቸው በሚመስሉና በፍፁም ክህደትና በህወሃታዊ ሴራ የተሞላ ፅሁፍ በአግባቡ መልስ መስጠትና እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ ህወሃትና ተላላኪዎቹ በታጋዩና ጀግናው ህዝባችን መካከል ሊዘራ ያሰበውን መርዛማ እንክርዳድ ነቅሶ በማውጣት ማጋለጥና ለወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ትክክለኛውን ታሪካዊ መረጃ ከምንጩ ማቅረብ አስፈላጊነቱ ስለታመነበት ይህ ታሪካዊ ሰነድ እንደተለመደው በስደት በሚገኙ የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆች አማካኝነት ተዘጋጅቶ ቀርቧል።  

በቅድሚያ ግን ለጠቅላላ ግንዛቤ ይረዳ ዘንድ እነዚህ ለህወሃት ፍርፋሪ የተንበረከኩና የወልቃይት ጠገዴን ማህበረሰብ ህወሃትን ለመሰለ “የቀን ጅብ” አሳልፈው የሰጡ ግለሰቦች እነማን እንደሆኑ ለአንባቢ በመጠኑም ቢሆን ግልፅ ማድረጉ አይከፋምና እነሆ ። ይህ ባንዳነት የባህሪው የሆነው የሆድ-አደሮቹ ቡድን የሚመራው በወ/ሮ አዜብ መስፍን ሲሆን፣ በእርሷ ገንዘብና ስልጣን ሙሉ ድጋፍና እንክብካቤ የሚደረግለት የአንድ ቤተሰብ ስብስብ ነው። አቶ ኃይሉ የሺወንድም ደግሞ ለረጅም ዘመናት በአውሮፓ ኖርዌይ አገር ነዋሪ የነበሩና ካለፉት ሁለት አመታት ወዲህ ግን ነዋሪነታቸውን በኢትዮጵያ ያደረጉ ሲሆን በቅርቡ ሁለት ሰፋፊ የእርሻ መሬቶች በጋንቤላ ውስጥ እንደተሰጣቸውና አዲስ ባለሃብት ለመሆን እየተሯሯጡ የሚገኙ ናቸው።እኒህ ግለሰብ የወ/ሮ አዜብ መስፍን ወንድም (የወ/ሮ አዜብ ምስፍን እናትና የአቶ ኃይሉ እናት እህታማቾች) ሲሆኑ እንዲሁም የትግራይ ነጻ አውጭ ግንባር ባለስልጣን የሆነው የአቶ ፈረደ የሺወንድምና  በካርቱም ሱዳን ውስጥ ስደተኞችን በመጠቆምና በማሳሰር በሰፊው የሚታማው የአቶ ተስፉ የሺወንድም ወንድም እንደሆኑ ይታወቃል። 

አቶ ኃይሉ አገር ቤት ከመግባታቸው በፊት የትግራይ ነጻ አውጭ ግንባር እንደ ወራሪ ኃይል ይመለከቱ እንደነበርና ወልቃይት ወደ ነበረበት ግዛት ወደ ጎንደር ያለ ድርድር መመለስ እንዳለበትም እንደአቋም  በመውሰድ ያስተጋቡ እንደነበር ይታወቃል። ሌላኛው ግብረ-በላ ደግሞ አቶ ፀጋዬ አስማማው የሚባል ሲሆን የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ በመሆን የሚያገለግልና የህወሃት ቀንደኛ አሽከርና ተላላኪ በመሆን ከአቶ ፈረደ ጋር ሰሜን አሜሪካ ድረስ በመምጣት የወልቃይት ተወላጆችን ሰብስበው የ“እራስ ገዝ” አስተዳደር እንዲጠይቁ ሲያግባባ የነበረና አሁንም በተሰጠው የዳኝነት ሙያ ሽፋን ታጋዩን ህዝባችንን በማስፈራራት ግንባር ቀደሙን ሚና የሚጫወት እርሱ ነው።  በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ላይና በተለይም “የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት” አስከባሪ ኮሚቴ ላይ ለሚደርሰው ማንኛውም እንግልት፣ እስር፣ ስቃይና፣ አደጋ ግንባር ቀደም ጠያቂዎቹ እነዚህ አራት ሆድ-አደሮች መሆናቸውን ለማሳሰብ እንወዳለን። 

 

መልካም ንባብ

ከአዘጋጆቹ

ወልቃይት ጠገዴ ማነው?

“የወልቃይት ባህልና የማንነት ጥያቄ” የሚለው ፅሁፋ በገጽ 4, 2ኛው አንቀጽ ላይ “ስለዚህ የትግራይ ነጻ አውጭ ግንባር ወልቃይትን ከተቆጣጠረበት ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያለውን ታሪክ በዜሮ ብናባዛው፤ የህዝበ-ውሳኔው ውጤት ከትግራይ ጋር መኖር የሚሹ ወልቃይቴዎች በሰፊ ልዩነት ሊያቸንፉ መቻላቸውን ያበስር ነበር” ይላል። ነገር ግን ይህ የአቶ ሃይሉ የሺወንድም ምኞትና ድምዳሜ ወይም ህወሃታዊ ተልዕኮ ከታሪክና ከተጨባጩ የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ አቋምና ምርጫ ፍጹም እንደሚቃረንና እንደሚጋጭ በሁለት ቀደምት የህወሃት አባላት የቀረቡ ምስክርነቶች አጥጋቢ መልስ ስለሚሰጡ እነርሱን እንመልከት።

ኢትዮጵያውያን እንደ ዛሬው ህወሃት በለጠፈብን የብሔር ታርጋ ምክንያት የጎሪጥ መተያየት ሳንጀምርና ሃገራችን ጎጥ ጎጥ ከመሽተቷ 37 ዓመታት በፊት በትግራይ ነጻ አውጭ ቡድን በኩል ለወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ የቀረበው “ወልቃይት ጠገዴ ማነው?” ጥያቄ በወቅቱ የነበሩት ኩሩና በማንነታቸው ላይ ፍጹም ብዥታ ያልነበራቸው ወገኖቻችን የህወሃት ወኪል ለነበረውና ጥያቄውን ይዞ ለመጣው ለአቶ መኮንን ዘለለው በማያዳግም ሁኔታ መልሰውለት እንደነበር ታሪክ ህያው ምስክር ነው። በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ የህወሃት ነባር አባልና የፋይናንስ ኋላፊ የነበሩት አቶ ገብረመድህን አርአያ በዲሴምበር 22, 2015 ኢትዮ-ሚዲያና ጎልጉል ድረ-ገፅ ላይ “በወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምት በአማራው ላይ ህወሃት የፈጸመው የዘር ማጽዳት ወንጀል” በሚል ባወጡት ጥልቅ ሰነድ በገጽ 2 ላይ፤

“በሪጅን 1 የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የነበረው፣ በአባቱ ወልቃይት ፀገዴ፣ በእናቱ ሽሬ የሆነው መኮንን ዘለለው፣ የተወጠነውን ትልእኮ ይዞ ወልቃይት ፀገዴ ፀለምት እየተዘዋወረ ህዝቡን በመሰብሰብ ይህ መሬት የትግራይ መሬት ስለሆነ እናንተ ከእንግዲህ ወዲህ የሰሜን ጎንደር ዜጎች አይደላችሁም፣ የትግራይ መሬት ስለሆነ እንኖራለን ካላችሁ ትግሬዎች መሆናችሁን አምናችሁ ተቀበሉ፤ የትግራይ ዜጎች አይደለንም፣ ሰሜን በጌምድር የትግራይ አይደለም ካላችሁ ደግሞ የድርጅቱን የህወሓትን ውሳኔ ተጠባባቁ፤ የምታምኑበትን አሁን ተናገሩ በማለት ሲያስጠነቅቅ፣ ከህዝቡ በኩል ያገኘው መልስ ግን አንድ ነበር። የቀረበውን ሃሳብ ከህፃን እስከ አዋቂ፣ የወልቃይት ፀገዴና የፀለምት ህዝብ፣ እኛ የሰሜን በጌምድር (ጎንደር) አማሮች እንጂ ትግሬዎች አይደለንም፣ የታሪካችን ስር መሰረቱ የበጌምድር አማሮች ነን። ይህ ቆመህ የምትናገርበት መሬት ሰሜን በጌምድር ይባላል። ከጥንቱ ታሪካችን 3 ብትነሳም ይህ መሬት ታሪካዊ ነው። ያለፉት የኢትዮጵያ ነገሥታት ከጥንት ጀምሮ እስከ አሁኗ ሰአት በመንግሥት እውቅና ያገኘ የጎንደር፣«”የበጌምድር” ጠቅላይ ግዛት እየተባለ የሚጠራ ነው። ዋና ከተማችን ደግሞ ጎንደር ነው። የእናንተም ትግራይ ጠቅላይ ግዛት ይባላል፣ ዋና ከተማው ደግሞ መቀሌ ነው። ስለዚህ ኣናንተ የተሓህት ታግዮች ጉዳዩን ብታሱብበት ጥሩ ነው። ወደ እርስ በርስ ግጭ ያመራል።በተጨማሪም ታሪካዊ የወሰን ክልል አለን፣ እሱም ተከዜ ወንዝ ነው። የትግራይና በጌምድር የድንበር ክልሉ ተከዜ ወንዝ ነው። ከጥንት ጀምሮ የሁለቱ ኢትዮጵያውያን የድንበር ወሰን መሆኑን ልናረጋግጥ እንፈልጋለን በማለት በአንድነት ድምፅ ህዝቡ ራሱ አረጋገጠ።” በማለት ገልፀውታል።

ይልቁንም በአቶ መኮንን ዘለለው በኩል ለቀረበላቸው የማንነት ጥያቄ “የበጌምድር አማሮች ነን” የሚለውን የማያወላዳ ምላሽ የሰጡ የማህበረሰቡ ታላላቅና የተከበሩ መሪዎች በአቶ ስዩም መስፍንና በአቶ ግደይ ዘራፅዮን መሪነት ታፍነው ወደ ትግራይ መወሰዳቸውንና በሳሞራ የኑስ ትእዛዝ እንደተረሸኑ እራሳቸው አቶ መኮንን ዘለለው ለኢሳት ቴሌቭዥን በሰጡት ቃለ-መጠይቅ ላይ በዝርዝር አጋልጠዋል። በዚህ “ወልቃይት ጠገዴ ማነው?” በሚለው የህወሃት ያልተቋረጠ ጥያቄ ዙሪያና ህዝባችን በሚሰጣቸው አንድ፤ ግልፅና ቀጥተኛ መልስ ምክንያት ወገናችን የጅምላ ግርፋቶች፤ መፈናቀሎች፤ እስራቶች፤ ግድያዎች፣ ስደቶች፣ ቅስም ሰባሪና፣ ፀያፍ በደሎች ተፈፅመውበታል።

ታዲያ ይህ ሁሉ ሰቆቃ አሁንም ሳያባራ የትግራዩ ነጻ አውጭ ቡድን እነሆ ዛሬም እንደገና በእነ አቶ ሃይሉ የሺወንድም በኩል “ወልቃይት ጠገዴ ማነው?” ይለናል። አስቀድሞ በአቶ መኮንን ዘለለው በኩል ቀርቦ ህዝባችንን ለእልቂት የዳረገው ህወሃታዊ ጥያቄ ዳግም ለወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ መጠየቅ ማለት አንድም ወገኖቻችን በማንነታቸው ጸንተው በመቆማቸው ምክንያት የከፈሉትን መስዋእትነት እንደ “ውሻ ደም” በመቁጠር ለመሳለቅ ወይም በህዝባችን ላይ ለተደገሰው ቀጣይ ህወሃታዊ ፍጅት ሰበብ ለማዛጋጀትና የጥፋት መንገድ ለመጥረግ የታለመ ይመስላል።

የህወሃት ሆድ-አደሮች ምን እያሉን ነው?

ወልቃይት ጠገዴ ማነው? ለሚለው የህወሃት መላዘን ወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ምላሹ ከላይ በአይን እማኞችና በህያው ምስክሮች እንደተረጋገጠ አይተናል። ታዲያ ለምን የዛሬዎቹ ተላላኪዎች “ስለዚህ የትግራይ ነጻ አውጭ ግንባር ወልቃይትን ከተቆጣጠረበት ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያለውን ታሪክ በዜሮ ብናባዛው፤ የህዝበ-ውሳኔው ውጤት ከትግራይ ጋር መኖር የሚሹ ወልቃይቴዎች በሰፊ ልዩነት ሊያቸንፉ መቻላቸውን ያበስር ነበር” እያሉ ሌላውን ህዝብ ለማደናገር ይሞክራሉ? ለምንስ በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ በደል ላይ ይዘባበታሉ? የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም።

ከዚህ የሆድ አደሮች ዘመቻ የምንረዳው ነገር ቢኖር ተላላኪዎቹ ቀደም ሲል በተደጋጋሚ እንገልጸው እንደነበረው ሁሉ ከህወሃት የተሰጣቸውን “የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብን በማዳከምና በመከፋፈል ትግሪያዊነትን አሜን ብሎ እንዲቀበል” የማስቻል ተልእኮ ለማሳካት በሚል በመላው ኢትዮጵያ በተለይም እንደ ጋምቤላ ባሉ አካባቢዎች በሚደረጉ የመሬት ዘረፋዎችና ቅርምቶች (ወልቃይት ጠገዴ ለትግራውያን ብቻ ነው) ቢንበሻበሹም ውጤቱ ግን “ጉም መዝገን” ሆኖባቸዋል። ይልቁንም በሃገር ውስጥ የሚገኘው የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ከምንግዜውም በላይ ተደራጅቶና ከመላው የአማራ ህዝብ ጋር አንድ ሆኖ ማንነቱ ለማስከበር ቆርጦና አምርሮ ሲነሳ ከህወሃት ይልቅ የተጨነቁት በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ስም ድርጎ ሲቀበሉ የከረሙት ናቸው።

ከህወሃት በኩል ልምጭ የተቆረጠበት የሚመስለው ሆድ-አደሩ ቡድን መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ያንገሸገሸውንና ህወሃትን እስከ አንገቱ ያነቀውን፤ ይልቁንም በህወሃት/ኢህአዴግ መንደር እውቅና አግኝቶ ከጠ/ሚ እስከ ተራ ካድሬ እየተቀባበለ የሚዘምርለትን “የመልካም አስተዳደር እጦት” በምትባል “የጦስ ዶሮ” በመታከክ የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ያነሳውን ዘርንና ትውልድን ከጥፋት የመታደግና የአማራ ማንነቱን በትግሪያዊነት ከመተካት የማዳን ፈርጀ ብዙ ጥያቄ “የትግራይ ክልል ባለስልጣናት የአስተዳደር በደል ስለፈጸሙበት” ነው እያሉ ማፌዝ በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ቁስል በእሳት የጋለ ብረት እንደመስደድ ይቆጠራል።ያስተዛዝባልም።

ይልቅስ አቶ ሃይሉና የጥቅም ተጋሪዎቻቸው በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ላይ የደረሰው በደል የዘር ማፅዳትና በትግሪያዊነት የመተካት ዓለም-አቀፍ ወንጀል መሆኑን የምትስቱት አይመስለንም። ይህን በማንነታችን ላይ የተፈጸመና በዓለም-አቀፍ የፍርድ አደባባይ የሚያስጠይቅን ወንጀል በማኮሰስና “የትግራይ ክልል ባለስልጣናት የአስተዳደር በደል” አድርጎ በማቅረብ ከህወሃት ጋር የገጠማችሁን ኪሳራ ማወራረድ ወይም የሚቆረጥላችሁን ድርጎ ማሳደግ አትችሉም። ኪሳራችሁን ማወራረድም ሆነ ሌላም ማድረግ የምትችሉት ለጌቶቻችሁ እውነቱን በመናገር ብቻ ነው። ምክንያቱም የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ጎንደሬ-አማራ መሆኑን በአንድ ድምጽ ያረጋገጠውና በማንነቱም ምክንያት ለሚመጣ ማንኛውም ነገር ዋጋ ለመክፈል ዝግጁነቱንና ቁርጠኝነቱን በተግባር ያሳየው ገና “የትግራይ” የሚባሉ ገዥዎችና አስተዳደራቸው ከመፈጠሩ እጅግ አስቀድሞ እንደነበር ከወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ባልተናነሰ እነ ስብሃት ነጋ ጠንቅቀው ያውቃሉና እራሳችሁን አታታልሉ። ትዝብት ላይም አትውደቁ።

በሌላ በኩል ምንም እንኳ ዛሬ ህወሃት እስከ አፍንጫው ቢታጠቅና የሃገሪቱን መንግስታዊ ስልጣንና ሃብት እንዳሻው ቢያዝና ቢናዘዝበትም የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ዛሬም በማንነቱ ላይ ያለውን የቀደመ ጽኑ እምነትና የትውልዱን ምስክርነት ማስለወጥ አልተቻለውም። እንግዲህ ለህወሃትና ለእነ አቶ ሃይሉ የሺወንድም እውነታው እንደ እሬት መራራ ቢሆንባቸውም ታሪክ በደማቁ የመዘገበውና በእያንዳንዱ የወልቃይት ጠገዴ ተወላጅ ህሊና ተጽፎ የሚገኘውና ለትውልድ የምናስተላልፈው እውነታ ግን የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ህወሃት ዕርስታችንን ከመርገጡ በፊትም ሆነ በወረራ በተቆጣጠረ ጊዜ በጎንደሬ-አማራነቱ ጸንቶ በመቆም መራር መስዋእትነት እንደከፈለ ሁሉ ወደፊትም በማንኛውም የከፋ ፈተና ውስጥ ቢያልፍም ከጎንደሬ-አማራነቱ ሊያናውጸው የሚችል ምንም አይነት ምድራዊ ሃይል ያለመኖሩን ነው። ምክንያቱም ወልቃይት ጠገዴ አይደለም ለማንነቱና ለዕርስቱ፤ አምነው ለተጠጉትም አንገት እንደማያስደፋ ትግራውያን ያውቃሉ!

ታዲያ ወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ማነው?

“በአፍ የመጣን በአፍ፣ በመጣፍ የመጣን በመጣፍ” መመለስ የቀደሙ አባቶቻችን ስርዓትና ብሂል በመሆኑና ታሪካዊ ጠላቶቻችንም እንደ አመጣጣቸው መመለስ ተገቢ በመሆኑ ህወሃት በተላላኪዎቹ በኩል በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ መካከል ሊዘራ የሞከረውን እንክርዳድና በኢትዮጵያ ህዝብና በታሪካችን ላይ ሊፈጠር የታሰብውን ብዥታ ለማጥራት ሲባልና ለታሪክም ምስክር ይሆን ዘንድ “የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ማነው?” የሚለውን ጥያቄ በአጭሩ እንደሚከተለው ስንመልስ ጥልቁንና ተነግሮ የማይጠገበውን የወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ታሪክ ለታሪክ ፀሃፊዎችና ለባለሙያዎች በመተው ነው።

  1. የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ እንደ ማንኛውም የሰሜኑ ኢትዮጵያ ማህበረሰብ ሁሉ የአካባቢውን ስያሜ በመውሰድ የእራሱ መጠሪያ አድርጎ ኖሯል። ለምሳሌ የጎንደሬ ዘሩ ምንድነው? የሚኖርበት አካባቢ ስያሜ ማን ይባላል? የጎጃሜውስ? የወሎዬው? የጋይንቴው? የምንጃሬው? የስሜንኛው? … ወዘተ ለመሆኑ እነዚህ ወገኖቻችን እራሳቸውን ሲጥሩ “እኛ ማነን” ይላሉ? እኛስ እነርሱን እነማን ናቸው እንላለን?  ጎንደሬውን – ጎንደሬ ፤ ጎጃሜውን – ጎጃሜ ፤ ወሎዬውን – ወሎዬ፣ ደብረታቦሬውን – ደብረታቦሬ፤ ጋይንቴውን – ጋይንቴ፤ ስሜንኛውን – ስሜንኛ፤ በለሴውን – በለሴ፣ ወግሬውን – ወገሬ፣ ቋረኛውን – ቋሬ …. ወዘተ እያልን ወልቃይቴውን – ወልቃይቴ፣ ጠገድቼውን – ጠገድቼ፣ ጠለምቴውን – ጠለምቴ አላልንምን? እንላለን እንጂ!
  1. ታዲያ የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ አባቱ ማነው? የዘር ሐረጉስ ከየት ይመዘዛል ቢሉ?

ወልቃይት የሚለው ስም ከስር መሰረቱ የአማራ መስራች አባት የሚባለው የተጠቀሰበት አገር ነው። አማራው ከወልቃይት ወደ ጠለምት ከዚያም ወደ ላኮ መልዛ (የዛሬው ወሎ) እያለ ሌላውን አካባቢ እያስፋፋ እስከ ሞቃዲሾ ተጉዞ ሃገር ያቀና ታላቅ ነገድ ያረፈበት መሆኑ ታሪክ ሁሌም ይመሰክራል። ወልቃይት ጠገዴ አማራ የሆነው ዛሬ ትግሬ ሊያደርጉት እንደሚታትሩት በተዘዋዋሪ ሳይሆን የአማራ አባትና ግንድ በመሆን ነው። ለዚህ ፅሁፍ በሚስማማ መልኩ ታሪካዊ ማስረጃዎችን እንመልከት።

አለቃ ታዬ ወልደማርያም የተባሉ ሊቅና የተመሰከረላቸው ታሪክ ፀሃፊ “የኢትዮጵያ ህዝብ ታሪክ” በተባለው ዝነኛ መፅሃፋቸው በገፅ 16 ላይ እንዲህ ፅፈዋል። “ከለው ከሳባ ወደ ምዕራብ ወደ ደቡብ ያለ ያማራ የወልቃይት የጠገዴ አባት ነው። ከእነዚህም የኢትዮጵስ ልጆች የወንድማማቾቹ ነገድ ህዝብ ሁሉ በመልካቸውና በቁርበታቸው ይመሳሰላሉ። እኒህም ህዝብ የያዙት አገር በጥቅሉ ባባታቸው ስም ኢትዮጵያ ተብሎ ይጠራል።” በመቀጠልም የአማራው አባት አስገዴ ግንዱ ከወልቃይት ጠገዴ አርማጭሆ ከዚያም እያደገና እየሰፋ አማራ ሳይንት ድረስ የደረስ መሆኑን ገልጸው ጽፈዋል።

አቶ አማረ አፈለ “ደም አይፍሰስ በቃ የህወሃት ማኒፌስቶ ያብቃ!” በሚለው መፅሐፋቸው በገጽ 27 ታሪካዊ ምስክርነታቸውን እንደሚከተለው አስፍረዋል።

“ከተከዜ ጀምሮ ወደ ደቡብ እስከ ሸላሎ በተዘረጋው ምድር ላይ ያሉት ወረዳዎች ሕዝቡ አፍ መፍቻ ቋንቋው አማርኛ ነው። ከትግራይ ጋር በተከዜ ወንዝ ድልድይነት ጎረቤት ስለሆነ ወዲያና ወዲህ ማዶ ያለው የዐማራና የትግራይ ቋንቋ ቃላት ቢያንስ 80 በመቶ ተመሳሳይ በመሆናቸው መናገሩ አዳጋች አይሆንባቸውም። ይልቁንም የወልቃይት ጠገዴና ጠለምት መዘጋዎች ጥጥ ስለሚያመርት ብዙ የትግራይ ተወላጆች በጥጥ ለቀማ ወቅት በየዓመቱ ወደነዚህ መዘጋዎች ይመጣሉ። ዐማሮች ከእነርሱ ጋር ለመግባባት ሲሉ ትግርኛውን ይጠቀሙበታል። ከእንግዶች መካከል ሀገሬውን አግብተው የሚቀሩም አይጠፉም። ለዚህም ወደ ኋላ መለስ ብለን ታሪክ ስንመረምር ወልቃይት ጠገዴና ጠለምት በአክሱም፤ በላስታው በሽዋ ሆነ በጎንደር ዘመነ መንግሥት አንድም ግዜ የትግራይ ግዛት አካል ወይም ገባር የሆነበት የታሪክ ወቅት የለም። ይህን እውነት ለመረዳት ከጎንደር ዘመነ መንግሥት በፊት ጀምሮ 20ኛ ምዕተ ዓመት ሁለተኛ አጋማሽ ድረስ የታወቁ የውጭ ሀገር ጉብኝዎችና ታሪክ ፀሐፊዎች በተለያዩ ክፍለ ዘመናት ኢትዮጵያን እየተዘዋወሩ ካዩ በኋላ ስለ ብሔረስቦችና ስለ አስተዳደር ክፍሎች የተውልን ጹሑፎችና ካርታዎች ህያው የታሪክ ማስረጃዎች ናቸው።”

“ለአብነት ያህል ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ፤ ጅምስ ብሩስ፤ ዶክተር ሚካኤል ረሥል፤ ማንስፊልድ ፓርኪንስ፤ ስቨንረንሰን ወዘተ…….የተባሉ ታዋቂ ተመራማሪዎች ለትውልድ ያበረከቷቸውን መጻሕፍት መመልከት ይቻላል። ይልቁስ የኢጣሊያን መንግሥት ኢትዮጵያን በ1928 ዓ/ም ከመውረሩ በፊት በጐንደር ከተማና በሌሎች ከተሞች በከፈታቸው የቆንስል ቢሮዎች አማካይነት ባካሄደው ሰፊ የኢትዮጵያ ብሔረሰቦች ጥናት ባወጣው አስተዳደር መዋቅር ትግራይ ከኤርትራ ጋር ሲደርብ ጠገዴንና ጠለምትን የአማራ ክልል በማድረግ ትግሬ አለመሆናቸውን አረጋግጧል።”

ወልቃይት ጠገዴ ፡ ትግሬ 

የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ለመላው ኢትዮጵያዊ ይልቁንም ለድንበርተኛ የትግራይ ህዝብ ያበረከታቸው ታሪካዊና ዘመን ተሻጋሪ ውለታዎች በትግራይ ህዝብ ሁሌም እንደሚታወሱና ከትውልድ ትውልድም እንደሚዘክራቸው በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡ ለምን ቢሉ እነዛ የትግራይ ህዝብን ህልውና የተፈታተኑ ክፉ የረሃብና ዘመናትና በእነዛ የጭንቅና የስደት ዘመናት የታደገን ጎረቤት መርሳት የማይታሰብ ነውና፡፡

ይሁንና ወራሪውና ተስፋፊው የትግራይ ነፃ አውጭ ቡድን በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ላይ እያደረሰ የሚገኘውን የዘር ማፅዳት ወንጀል የበቀል ሽፋን ለመሰጠትና የትግራይም ህዝብ የዚህ እኩይ ሴራ አካል በማስመሰል እጅግ የተዛቡና አኩሪ ታሪካችንን የሚያጎድፉ  አሉባልታዎችና የፈጠራ ታሪኮች በህወሃት መንደር ከመወራት አልፈው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ለህወሃት በተንበረከኩና ባደሩ የአንድ ቤተሰብ አባላት ፊታውራሪነት ወደ ህዝብ በነጻ ሚዲያዎች አማካኝነት በፅሁፍ ሲሰራጩ ለመመልከት ችለናል፡፡

አበው “ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል” እንዲሉ ይህን እኩይ ሴራ ከወዲሁ በማጋለጥ በህዝቦች መካከል ሊፈጠር የታሰበውን ውዥንብርና ህወሃታዊ ትርፍ ማኮላሸት አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡

ውንጀላ 1. “የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ የትግራይን ህዝብ ይንቃል (ዝቅ አድርጎ ይመለከታል)” ስለመባሉ፤

ምንም እንኳ እነ አቶ ሃይሉ የሺወንድም በፅሁፋቸው በገፅ 4 ላይ የትግራይን ህዝብ በወልቃይት ማህበረሰብ እንደተበደለና በደሉን “ህወሃቶች መች እረሱ?” እያሉ በማጠየቅ ለህወሃት የፈጠራ ውንጀላ ማረጋገጫ መሰል ሃሳብ ቢያዋጡም እኛ ግን ይህን ሃሰተኛ ክስ በሁለት ዋና ዋና አቅጣጫ በማየት ለከሳሾቻችንና ለአጫፋሪዎቻቸው ምላሽ ለመስጠት እንሻለን።

“ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ፣ ይሏታል ጅግራ”

“የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ትግሬ ነው” ለዚህም ነው ወደ ትግራይ የከለልነው እያሉ አይናቸውን በጨው አጥበው ከ25 ዓመታት በላይ የሚያደርቁን ህወሃቶች፤ በሌላ በኩል ደግሞ “የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ የትግራይን ህዝብ ይንቃል” በማለት ደጋግመው ይከሳሉ።

ለመሆኑ ከመቼ ጀምሮ ነው አንድ ህዝብ እራሱን የሚንቀው ወይም የእራሱን ዘር ዝቅ አድርጎ የሚመለከተው? እውነት የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብና የትግራይ ህዝብ አንድ ዘር ነው ተብሎ ቢታመን ኖሮ ይንቀናል ወይም ዝቅ አድርጎ ይመለከተናል ሊባል ይቻል ነበርን? እውነታው ግን፦

  1. በትግራይ ነፃ አውጭ ቡድን የትግራይ ህዝብ ጠላት ተደርጎ በተቆጠረውና ሃገር አቀፍ የዘር ፍጅት የታወጀበት የአማራው ነገድ አካል በመሆኑና የዘር ማፅዳቱ ዘመቻ የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብን የሚያካትት በመሆኑ ሲሆን፤
  1. በሌላ በኩል ደግሞ ለ“ታላቋ ትግራይ” መንግስትና ለ“ትግሪያዊው ወርቅ” ህዝብ የምግብ ዋስትና የሚያረጋግጥ ለም መሬትና ከቀሪው ዓለም  ከሱዳን ጋር የሚገናኙበት የየብስ መውጫና መግቢያ  መስመር ለማግኘት በመቋመጥ የተነደፈውን የ1968ቱን የህወሃት ማኒፌስቶ ስኬት ሊያደናቅፍ ይችላል በሚል እሳቤ ለፈጸሙት የወልቃይት ጠገዴን ዘር የማፅዳትና በትግሪያዊነት የመተካት ወንጃል ምክንያታዊ ለማስመሰል የተለጠፈ የበቀል ካባ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
  1. ይልቁንም ታሪክና ትውልድ ይቅር ለማይለውና ዓለም ለተፀየፈው የወልቃይት ጠገዴን ዘር የማፅዳትና በትግሪያዊነት የመተካት ወንጀላቸው በህዝባችን የተቀናጀ መራራ ትግል ሲከሽፍና ከተጠያቂነት እንደማያመለጡ ሲረዱት፤ በደሉን ለትግራይ ህዝብ ክብር ሲሉ የፈፀሙት ለማስመሰልና፣  የትግራይ ህዝብም የዚህ እኩይ ወንጀላቸው ተባባሪ እንደሆነ የማስመሰል ሴራ አካል ስትሆን፤ በላዩም ላይ ተላላኪዎቻቸው “ህወሃቶች መች እረሱ?….” በማለት ልክ የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ የትግራይን ህዝብ ይንቅ እንደነበርና አሁን ህወሃቶች በደሉን መርሳት ሲገባቸው ነገር ግን እንዳልረሱት በማስመሰል ማረጋገጫ ይሁን ትዝብትነቱ ያለየለት ለህወሃት የፈጠራ ክስ የሃሰት ምስክርነታቸውን ይሰጣሉ፡፡

ውንጀላ 2.  “የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ በ50/60ዎቹ ዓ.ም አካባቢ ወደ አካባቢው ለተለያዩ የጉልበትና የግብርና ስራዎች ይመጡ    የነበሩትን የትግራይ ተወላጆች ያገለገሉበትን ገንዘብ ባለመክፈል ይበድላሉ” ስለመባሉ፤

ዛሬ በዚህ ጉዳይ ላይ መልስ መስጠት አላስፈላጊ እንደሆነ እናምናለን፡፡ ምክንያቱም ህዝባችን በፊውዳሉ ዘመን በአሰሪና ሰራተኛ መካከል ሊከሰቱ ከሚችሉ ከእንዲህ አይነቱ ተራና ታሳቢ ከሆኑ ክሶች በላይ እጅግ አንገብጋቢና አሳሳቢ በሆኑት የህወሃትና የተላላኪዎቹ ሴራዎች ላይ በናተኩርና በወገናችን መካከል በሚያሰራጯቸው በማር የተለወሱ መርዞች ላይ በማተኮር ከዘር ማፅዳቱ ወንጃል በብዙ መስዋዕትነት ያተረፈውን ትውልዱን ከብከላ እንድንከላከልለት ቅድሚያ እንደሚሰጥ ጠንቅቀን እናውቃለንና ነው፡፡

ነገር ግን ከ1969 ዓ.ም በኃላ ላለው አዲስና ለመጭው ትውልድ የአባቶቹንና የአያቶቹን አኩሪ ታሪክ እግረ መንገዱን እንዲያውቅና ከሁመራ የእርሻ ልማት ጋር ተያይዞ ለሚነሱ መጥፎም ይሁን ጥሩ ታሪኮች እውነተኛ ስንቅ ከምንጩ ማቀበል ተገቢ ነው በሚል በዚህ ውንጀላ ዙሪያ ትንሽ ለማለት ወደድን፡፡

የወልቃይት ጠገዴ አብዛኛው ህዝብ በግብርና ሙያ የሚተዳደር የነበረ ሲሆን የወባ በሽታን፣ ጊንጥና እባብን …ወዘተ ተቋቁሞ  መዘጋ ወልቃይትንና ሁመራን የመሰሉ ገናና የእርሻ ቦታዎችን አልምቷል። ያለማውን መሬትም “መውፈር ቀደም” ስርአት በመጠቀም ለሁሉም አራሽ ክፍት በማድረግ ከመላው ኢትዮጵያዊ ወገኑ በተለይም ደግሞ ከኤርትራና ከትግራይ ህዝብ ጋር ተካፍሎ ሲያርስ ኖራል። በወቅቱም በብዙ ሺ ለሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች ጥጥ ለቀማና ማሽላ ቆርጣ ከመሳሰሉ ዝቅተኛ ደረጃ የስራ እድሎች እስከ ባለ መሬትነት ባሉ የልማት ዘርፎች ይሳተፍ ነበር።

በሌላ በኩል ደግሞ የወልቃይት ጠገዴ  ማህበረሰብ ትግራይ ውስጥ በተደጋጋሚ ርሀብ በተከሰተባቸው በእነዛ ክፉ ዘመናት ነብሳቸውን ለማትረፍ በስደት ለሚመጡት በብዙ ሺዎች ለሚቆጠሩ የትግራይ ወገኖች ጊዚያዊ መጠለያና ምግብ በማቅረብ እንዲያገግሙ ካደረገ በኋላም ራሳቸውን መልሰው እንዲያቋቁሙ የስራ እድል በመስጠት ሲረዳ የቆዬ የወገን አለኝታ ነበር።

እንግዲህ በዚህ ወቅት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆችና የአካባቢው ህዝብ በሚሳተፍበት የእርሻ ልማት በግለሰቦች ደረጃ ለሚፈጠሩ የአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነቶች እንዴት የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ተጠያቂ ሊሆን ይችላል?

እውነታው ግን እራሱን የትግራይ ነጻ አውጭ ብሎ የሰየመው ወራሪና ተስፋፊ ቡድን ለተዘፈቀባቸው የዘር ማፅዳት፣ የዝርፊያ፣ ኢትዮጵያን የማፈራረስና፣ አካባቢውን የማተራመስ ወንጀሎች በመላው የኢትዮጵያ ህዝብና በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ከሚጠብቀው ፍርድ ለማምለጥ ከለላና ዋሻ በማድረግ የሚጠቀምበትን የትግራይ ህዝብ በመያዦነት ይዞ ለመቆየት በማለምና በተለይም አጎራባች ከሆኑት የጎንደርና የኤርትራ ህዝብ ጋር በጠላትነት እንዲተያይና በስጋት ውስጥ ሆኖ ህወሃትን ብቻ እያመለከና ለህወሃት ሹማምንት እየተገዛ እንዲኖር የተጠመደበት ወጥመድ አካል እንጂ ውንጀላው የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ከትግራይ ህዝብ ጋር የነበረውን ግንኙነት በትክክል ያላገናዘበና የግንኙነቱንም ልክ አቆሽሾ የሚገልፅ የሃሰት ውንጀላ ነው።

ለትግራይ ሲቆርሱ አያሳንሱ 

ይህ ለሆዱ ያደረ ቡድን የትግራይ ነፃ አውጭ ቡድን  በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ላይ በመፈፀም ላይ የሚገኘውን የዘር ማፅዳትና አካባቢውን በትግሪያዊነት የመተካት ወንጀል መቃወምና ማውገዝ ሲሳናችውና ይልቁንም አገር ያወቀውንና ፀሃይ የሞቀውን የህወሃት ወንጀል በትግራይ ህዝብ የተፈጸመ በማስመሰል “የወልቃይትን ህዝብ ሰብአዊ ክብር የሚያዋርዱ ጥሰቶችን በዚህ መድረክ ላይ መግለፁ በህዝቦች መካከል አላስፈላጊ ቁርሾ ስለሚፈጥር እዛው ተከድኖ ይብሰል ብለናል” በማለት ከትግራይ ህዝብ ይልቅ ለህወሃት ሹማምንት ያላቸውን ወገንተኝነትና ታዛዥነት ያረጋግጣሉ።

በሌላ በኩል ግን በትግራይ ህዝብና በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ መካከል ጠላትነት እንዳይፈጠርና ቁርሾ ለትውልድ ላለማስተላለፍ በሚል ያደረጉትን “ጥንቃቄ” እና “አስተዋይነት” በእጅጉ አድንቀናል። አንድም ትላንት የፊውዳሉ ስርዓት ፈጸመ ለሚባለው ግፍና በደል ዛሬ ተከሳሽና እዳ ከፋይ የተደረገው ጭቁኑ የአማራ ህዝብ ነውና ነገም የትግራይ ህዝብ የህወሃት ሹማምንት እዳ ከፋይ እንዳይሆን ቅድመ ጥንቃቄ መደረጉ ተገቢ ነው ።

ለወልቃይት አባት ፍለጋ፡ ከትግሪያዊነት ወደ ኤርትራዊነት መንሸራተት

የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሠብ እንደ ማንኛውም የሰው ዘር መነሻዬ የሚለው አባት፣ የእኔ የሚለውና ቆጥሮ የሚደርስበት የዘር ሃረግ፣ ይልቁንም የእኔ የሚላቸውን ታሪኮቹንና ባህሎቹን የሚመዘግብበትና የሚጠብቅበት ብሎም ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚያስተላልፍበት የእራሱ መንገድ ያለው ታላቅና አስተዋይ ህዝብ ነው። በአጭሩ ወልቃይት ጠገዴ አባቱን ያውቃል።

ነገር ግን እንደ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ማንነቱን ላይ ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባና የከፋ አደጋ ላይ የሚጥል ተግዳሮት የገጠመው በታሪኩ ለመጀመሪያ ግዜ በትግራይ ነፃ አውጭ ቡድን በኩል ወረራ ከተፈፀመበት ግዜ ጀምሮ ነው። ይህን ታሪካዊ ፈተና ለማለፍና በድል ለመወጣት ይቻል ዘንድ ወገናችን እልህ አስጨራሽ የሆነ መስዋዕትነት ከፍሏል። በመክፈልም ላይ ይገኛል።

በእነዚህ የታሪካችን የጨለማ ዘመናት በዋናነት የተጋፈጥነው ተግዳሮት ትግሬነትን እንደ ማንነታችን በመቀበል ትግሬ መሆን እና ከህወሃት ጋር ተመሳስሎ በመኖር ትግሬነትን ለትውልድ ማውረስ ወይም በአማራ ማንነታችን ፀንተን በመቆም ያለልካችን በህወሃት የተሰፋልንን ትግሬነት ባለመቀበላችን ምክንያት በጠላት በኩል ሊመጣ ያለውን ሁሉ መከራና ችግር በመጋፈጥ በማንነታችን ላይ ያነጣጠረውን ጠላት ድል መንሳት ነበሩ።

ከዚህም በመነሳት እነሆ ወገናችን ለአለፉት 37 ዓመታት በህወሃት የጭካኔና የመከራ ወጀብ ውስጥ ለማለፍ ቢገደድም የህወሃት ትግሪያዊነት የአንድም ወልቃይቴ ወይም ጠገድቼ ልብ ማማለልና ትግሬያዊ ማድረግ አልተቻለውም። እንግዲህ ሁሉም ህወሃታዊ ሴራዎች ተጨፍልቀው በግለሠብ ደረጃ የአንድን ወልቃይቴ ወይም ጠገድቼ ቀልብ መማረክ ካልተቻለው እንዴትስ አድርጐ የዚህን ኩሩና ታላቅ ህዝብ ማንነት ማስለወጥ ይቻለዋል? እንዴትስ አድርጐ ወልቃይት ጠገዴ የትግራያዊነት ቀሚስ ማልበስ ይቻላል። ለዚህም ይመስላል ሆድ-አደሮቹ በፅሁፋቸው በገፅ 2/4 አንቀፅ 2 ላይ “ትግሪያዊነት በትግራይ ክልል ባለስልጣናት በኩል በወልቃይት ማህበረስብ የተጫነ…” መሆኑን በማለት ማስተባበያ አይሉት ማስተዛዘኛ ለመስጠት የሞከሩት። ይልቁንም አበው “የጨነቀው እርጉዝ ያገባል” እንዲሉ የትግራይ ጌቶቻቸውን ለማፅናናት በሚመስል ቃና የወልቃይት ጠገዴን ማንነት ከ“ትግራይ-ትግራያዊነት” ወደ “ኤርትራ-ትግሪያዊነት” ለማንሸራተት የተገደዱት። እንዲህም ይላሉ፦

“ከትግራይ ብሄረሰብ ጋር የሚመሳሰለው በቀጥታ ሳይሆን በተዘዋዋሪ መንገድ ነው። ይኅውም የወልቃይት ባህል የሚመሳሰለው ኤርትራ ነጻነቷን ስትቀዳጅ አብሮ ከተገነጠለው ትግርኛ ከተባለው የከበሳ አካባቢ ብሄረሰብ ባህል ጋር ነው። በቋንቋም ቢሆን የትግርኛ ዘዬ ወይም ዳያሌክት ተመሳሳይነቱ ከኤርትራ ትግርኛ ጋር ነው።”

እውነታው ግን ዛሬ ተከዜን አሻግረን አርቀን ወደ ኤርትራ-ትግሪያዊነት እንደ ወረወርናቸው ሁሉ በቀጣይ የህዝባችን ጠንካራና የተባበረ ብርቱ ክንድ ሲደቁሳቸውና አዲሲቷ ማንነታቸው ገዥ አጥታ እርቃኗን ስትቀር እንደ ሌሎቹ ቀይባህርን ተሻግረው “የወልቃይት ጠገዴ ዘር የመጣው ከማዳጋስካር ነው” እንደሚሉን አንጠራጠርም። ለምን ቢሉ እንደ ዛሬ አያድርገውና ታላላቅ የሚባሉት ብሄሮች ሳይቀር “ከማዳጋስካር ነው የመጣነው” የምትለውን የህወሃት የዘረኝነት ድርሳን እያነበነቡ ያደነቁሩን ነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው።

ወልቃይት ጠገዴ ፡ አማራ

የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ባሳለፋቸው መራር የትግል ዘመናት እንደ ማንኛውም ትግል በተለያዩ የእድገት ደረጃዎች ውስጥ ማለፉ የግድ ነበር። ምንም እንኳ ትግላችን ከፊት ለፊቱ ከፍተኛና ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ የሚጠብቀው ቢሆንም በአሁን ሰዓት የህዝባችን ትግል ከፍተኛ የስኬት ደረጃ ላይ ይገኛል። ይሃውም ፦

  1. ህዝባችን ለአለፉት 37 ዓመታት በትግራይ ነፃ አውጭ ቡድን ከደረሰበት ፈርጀ ብዙ የዘር ማፅዳትና አካባቢውን በትግሪያዊነት የመተካት የተቀነባበረ ወንጀል የተረፉትን ልጆቹን በማሰባሰብና ወጣት የልጅ ልጆቹን የትግሉ አካል በማድረግ ለህልውናውና ለማንነቱ መጠበቅ ተከታታይ የሞት ሽረት ትግል የሚያደርግበት ቀውጢ ሰአት በመሆኑ፣
  1. የትግራዩ ነፃ አውጭ ቡድን ለአለፉት 25 ዓመታት የሃገሪቱን መንግስታዊ ስልጣን በመጠቀም አካባቢውን ከጋዜጠኞችና መንግስታዊ ካልሆኑ ምግባረ-ሰናይ ድርጅቶች እይታና እንቅስቃሴ ዝግ በማድረግ በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ላይ ይፈጽም የነበረው የተቀነባበረ የዘር ማጽዳት ወንጀል ለህወሃት ፍርፋሪ ባልተንበረከኩ ፅኑ ልጆቹ ያላስለሰ ትግልና በኢትዮጵያ የቁርጥ ልጆች ሁለገብ ድጋፍ በኢትዮጵያ ህዝብና በመላው ዓለም እውቅና ያገኘበትና የአብዛኛው ጋዜጠኞች፣ ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤቶችና፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እንዲሁም ሌሎች በንቃት የሚከታተሉት ግንባር ቀደም ጉዳይ ለመሆን የቻለበት ወቅት በመሆኑ፣
  1. ኢትዮጵያ ሃገራችንና ህዝቧን እያሸበረና እየዘረፈ የሚገኘው የትግራዩን ነፃ አውጭ ቡድን ከስልጣን ለማስወገድ በሰላማዊም ሆነ ነፍጥ አንስተው የሚታገሉ ኢትዮጵያዊ የፖለቲካ ድርጅቶች በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ላይ የደረሰበትን ፈርጀ ብዙ የዘር ማፅዳትና አካባቢውን በትግሪያዊነት የመተካት የተቀነባበረ ህወሃታዊ ወንጀል እውቅና የሰጡበትና ግንባር ቀደም የሚታገሉለት አጀንዳቸው በማድረግ በችግሩ አፈታትም ዙሪያ ግልጽ የሆነ አቋም የያዙበት ወቅት በመሆኑና፣
  1. በተለይም ከላይ የተዘረዘሩትንና በተለያዩ መድረኮች ያስመዘገባቸውን የተለያዩ ድሎች በማስጠበቅ መላውን የጎንደርና የአማራ ህዝብ ከጎኑ በማሰለፍ ለሚታገልለትና ለሚታገልበት የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ጥያቄ! መመለስ ከምንግዜውም በላይ ቆርጦ የተነሳበት ወሳኝ የትግል ወቅት ነው።

እንግዲህ በዚህ ወቅት ነው ሆድ-አደሩ ቡድን የህወሃት ጌቶቻቸውን ለማስደሰትና ከተቻላቸውም ጠራርጎ ሊወስዳቸው ከመጣው የህዝብ ቁጣ ለመታደግ መታተራቸውን በሚያሳብቅ መልኩ “ወልቃይት እና አማራ” በሚለው የመጣጥፋቸው 2ኛው አንቀጽ ላይ “ከቋንቋ ልዩነት ሌላ ወልቃይትን ከአማራ የሚያራርቅ ብዙ ግፍ ተፈጽሞል” በማለት ቀደም ሲል “ወልቃይት እና ትግራይ” በሚለው ክፍል “በህዝቦች መካከል ሰላም ለማውረድና አላስፈላጊ ቁርሾን ለትውልድ ላለማስተላለፍ” በማለት የተመፃደቁበትን ለህዝቦች ሰላም ያላቸው አርቆ አሳቢነታቸውንና ሚዛናዊ የሚመስለው ህሊናቸው ከመቅፅበት ከድቷቸው የጎንደር/አማራ ህዝብ በወልቃይት ላይ አደረሰ የሚሉትን ሁሉ በማተት የቆሙለትና ያደሩለትን ባንዳዊ አጀንዳ ምን ድረስ እንደሆነ ያሳዩናል፡፡

ይህ ሴራ የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ጥያቄ! አጀንዳን ከታጋዩ ህዝባችን በማስጣልና እርስ በእርሱ በመከፋፈል ለከፋው የህወሃት አፀፋዊ ጥቃት ያለ አጋርና ደጀን አጋልጦ ለመስጠት የተጠነሰሰ ህወሃታዊ ሴራ መሆኑን ለመረዳት ህወሃት ቀደም ሲል በህዝባችን መካከል ሰረጎ በመግባት የሄደባቸውን መሰሪ የከፋፍለህ-ግዛ መንገዶች ወደ ኃላ መለስ ብሎ ማየቱ በቂ ነው፡፡

ስለሆነም ከነበረን ልምድና ከቀደመው ታሪካችን በመነሳት ይህን በተንበርካኪው ቡድን በኩል የቀረበልንን ህወሃታዊ ሴራ ለህዝባችንና ከጎናችን ለተሰለፈው ለኢትዮጵያ ህዝብና በተለይም ለጎንደርና ለአማራ ህዝብ ጠለቅ ብሎ በማሳየት ህወሃትን በተባበረ የህዝብ ክንድ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስወገድ በሚደረገው ትግል የበኩላችንን ለማበርከት እንሻለን።

1ሴራ፡  የአማራን ህዝብ በፈጠራ ክስ መወንጀል

የአማራ ማንነት ጥያቄ! አጃንዳን ማስጣል

  1. ፀሃፊው “ወልቃይትና አማራ” የሚለውን ርዕስ መጻፍ ሲጀምሩ “ሲጀመር ወልቃይት የጎንደር እንጂ የአማራ ሆና አታውቅም” በማለት ነበር። እኛም እውነት ነው ወልቃይት የጎንደር እንጂ የማንም ሆና አታውቅም!!!!

ለአለፉት 25 ዓመታት ወልቃይት ጠገዴ የትግራይ አካል ነው እያለ ሲያደነቁረን የነበረው እርስዎ ዛሬ የተንበረከኩለት የትግራይ ነፃ አውጭ ቡድንና ከእርስዎ ቀደመው ለህወሃት ያደሩት ቤተሰቦችዎ ናቸው። ይልቁንም ታላቋን ኢትዮጵያ በቋንቋ ሸንሽኖ በአራቱም ማእዘን የዘር ግጭት የለኮሰው እርስዎ ያደሩለትና የተወዳጁት ህወሃት ነው። ጎንደርንም አማራ ብሎ የከለለው የእርስዎ ህወሃት እንጂ ሌላ ማንም አይደለምና ከሰማዎት እንደ ወዳጅነትዎ ለደንቆሮው ህወሃት “ወልቃይት ጠገዴ የጎንደር እንጂ … ሆና አታውቅም” ብለዋል ይበሉልን።

 

  1. በ2ኛው አንቀጽ ላይም “ከቋንቋ ልዩነት ሌላ ወልቃይትን ከአማራ የሚያራርቅ ብዙ ግፍ ተፈጽሞል” ይላሉ።

ከዚህ ዓረፍተነገር ጀምሮ የተከተላችው አንባቢ ሁሉ በእርግጠኝነት አንድ እውነት ያስታውሳል። ይኅውም ህወሃት በአለፉት 25 ዓመታት የስልጣን ዘመኑ የአማራውን ህዝብ ከኤርትራው፣ ከኦሮሞው፣ ከሲዳሞው፣ ከወላይታው፣ ከትግሬው፣ ከጋምቤላው፣ …ወዘተ ለማፋጀት የቀሰቀሰበትና ብዙ የአማራ ተወላጆች ለከፋ እልቂትና ስቃይ የተዳረጉበትን የህወሃት በአማራ ህዝብ ላይ የከፈተውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ ቅስቀሳ ያስታውሳል።

እንግዲህ ይህ በአቶ ሃይሉ የሺወንድም ፊታውራሪነት የቀረበው ደግሞ “የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ በአማራ ህዝብ ላይ …” በሚል ወደፊት ህወሃት በጎንደር ህዝብ ላይ በተለይም አማራነን ባሉ የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆች ላይ ለሚያካሂደው ጭፍጨፋ መንገድ እየተጠረገ መሆኑን እንረዳለን። ለዚህም ፍጅት ቅድመ ዝግጅት አቶ ሃይሉ በፅሁፋቸው የድርሻቸውን ተወጥተዋል።

  1. ጉደኛው ፀሃፊ “በሁመራ ዘመናዊ እርሻ ምክንያት ሲገኝ የነበረው ገቢ ለደብረታቦር ትምህርት ቤት መስሪያና ለሌሎች አካባቢዎች ጥቅም ይውል ነበር። አሁን እንደሚደረገው ማለት ነው” ይሉናል።

የሁመራ እርሻ ልማት የተጀመረው በ1950ዎቹ መጀመሪያ ሲሆን አገልግሎቱ የተቋረጠው “ገስጥ” ይባል የነበረው የደርግ ጦር በ1969 ዓ.ም ሁመራንና አካባቢውን በሃይል በወረረበትና ህዝባችንን በጀምላ በጨረሰበት ጊዜ ነበር።

በአንፃሩ ደግሞ ዛሬ በህወሃት የሚመራው የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር በሚያወጣው አመታዊ መጽሄት በአስተዳደሩ ስር የሚገኙ ት/ቤቶችን አስመልክቶ ያውጣውን መረጃ ምን እንደሚል በከፊል እንመልከት።

Screen Shot 2016-01-28 at 10.32.28 PM

ከላይ በተጨባጭ መረጃ እንደምንመለከተው የሁመራ እርሻ ልማት ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ እስከ ከሰመበት ጊዜ ድረስ  በደብረታቦር አውራጃ ምንም አይነት ት/ቤት እንዳልተገነባ የተረጋገጠ እውነት ሆኖ እናገኘዋለን።

ታዲያ የዚህ “ከሁመራ እርሻ በተሰበሰበ ግብር … ደብረታቦር ላይ ት/ቤት ይሰራ ነበር… ።አሁን እንደሚደረገው ማለት ነው።” የሚለው የሆድ-አደሩ ቡድን ውንጀላ መነሻው መሰረተ ቢስ እንደሆነ በተጨባጭ የተረጋገጠ ሲሆን ታዲያ የዚህ ውንጀላ ዋና አላማ ምን ሊሆን ይችላል ብሎ መመርመር ተገቢ ነው። ከህወሃት ባህሪና እስከዛሬ ካለፍንባቸው ተሞክሮዎች በመነሳት በእርግጠኝነት መናገር የምንችለው፦

  1. ህወሃት በአለፉት 25 ዓመታት የጎንደርን ህዝብ ሰሜንና ደቡብ ብሎ በመከፋፈል የማንወጣው የመጠላለፍና የመፋጠጥ አዙሪት ውስጥ ለመክተት አበክሮ ሰርቷል። አላማውም ይህ የታላቋ ኢትዮጵያ ጠባቂና ተቆርቋሪ የሆነውን ህዝባችን ከኢትዮጵያ ላይ አይኑን እንዲያነሳና ለህወሃት ዝርፊያና ኢትዮጵያን የማተራመስና የማፍረስ ሴራ እንቅፋት እንዳይሆን በማለም ነበር። ነገር ግን በህዝባችን አስተዋይነትና በታላላቆቻችን ብርቱ ጥረት ሴራው ለጊዜው ሊከሸፋና ውጤት ማምጣት ሳይችል ቀርቷል። እነሆ ይህ በሆድ-አደሩ ቡድን የሚቀርበው የፈጠራ ውንጀላ የሴራው ቀጣይ ክፍል ነው።
  1. የህወሃት የ37 ዓመታት የዘር ማፅዳትና በትግሪያዊነት የመተካት ወንጀል ያልተሳካውና ይልቁንም ህወሃትን እስከ አንገቱ ያነቀው የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ የአማራ ማንነት ትግል እዚህ ደረጃ ላይ የደረሰው በመላው የጎንደር ህዝብ ድጋፍና ተሳትፎ ጭምር ነው። ይህ እውነታ በህወሃት መንደር ግልፅ ከሆነ ሰነባብቷል።  ስለዚህም ህወሃት በለመደው ከአያቶቹ በወረሰው የከፋፍለህ ግዛ ፈሊጡ ተላላኪዎቹን በመጠቀም የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብን ከአማራ ህዝብና በተለይም ከጎንደር ህዝብ ለመነጠልና ለማጥቃት የተደረገ ሴራ አካል ነው።
  2. “…አሁን እንደሚደረገው ማለት ነው።” ይላሉ።

ዛሬ ህወሃት የወልቃይት ጠገዴን መሬት በመውረር የሚፈፀመውን ለከት ያጣ ዝርፊያ ወንጃል በዘውዳዊው ስርዓት ወቅት እንደሚደረገው አይነት ነው ብሎ በንፅፅር ማቅረብ አንድም የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ በህወሃት አልጠግብ ባይነትና አይን ያወጣ ዝርፊያ ምክንያት ህዝባችን የገባበት የበይ ተመልካችነትና የድህነት አረንቋ ላይ መዘባበት ሲሆን ይህም እጅግ አሳፋሪም ነውረኛም ነው። ፍርዱንም የትግራዩ ነፃ አውጭ ቡድን ዕርስታቸውን በመውረርና ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የትግራይ ሰፋሪዎችን የእርሻ መሬታቸው ላይ በማስፈር ለማያውቁት ረሃብና ልመና ለተዳረጉ የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆች እንተዋለን።

  1. ፀሃፊው ውንጀላውን በመቀጠልም “በደጃዝማች አያሌው ብሩ ግዛት ዘመን በወገራ ደጋማና ቆላማ አካባቢ የሚኖሩ አማራዎች በወልቃይት ላይ ወረራዎችና ዝርፊያዎች እንዲያካሂዱ ተደርጓል።” ይሉናል።

እንደሚታወቀው የፊውዳሉ ስራአት አንድን ለስርአቱ አልገዛ ወይም አልገብር ያለን ወረዳ ለመቅጣትና ለማስገበር ይጠቀምበት የነበረው አይነተኛ ዘዴ ሌላውን አጎራባች ወረዳ እንዲዘምትበትና እንዲወረው ብሎም እንዲያስገብረው በማድረግ ነበር። ይህም ድርጊት በተለያዩ የጎንደር አካባቢዎች ስለመፈጸማቸው በህይወት የሚገኙ አባቶቻችንና እናቶቻችን ህያው ምስክር ናቸው። ነገር ግን ይህን ዘርንም ሆነ ማንነትን መሰረት ሳያደርግ ይደረግ የነበረን መንግስታዊ ቅጣት “የጎንደር አማራዎች” በተለይ በወልቃይት ላይ ሆን ብለው የፈጸሙት አድርጎ ማቅረብ ህወሃት የጎንደርን ህዝብ እርስ በእርሱ ለማጋጨት ከጠነሰሰው ሴራ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?

እዚህ ላይ አንድ የታሪክ ማስረጃን ጠቅሰን እንለፍ። በ1949 ዓ.ም አካባቢ አዲስ ዘመን/ይፋግ አካባቢ አቶ አግማሱ ወጤ የተባለ ግለሰብ ያምፃል (ይሸፍታል)። ከእለታት በአንዱ ቀን ሊይዙት ከመጡ ወታደሮች ጋር ይታኮሳሉ። በዚህ ጊዜ የወረዳው አስትዳዳሪ የነበሩት ፊታውራሪ (ደጃዝማች) በረደድ አስፋው አቶ አግማሱ ወጤ እንዲያዝ እርዳታ ስላልሰጡ እርሳቸው የሚያስተዳድሩት ወረዳ እንዲወረር ይደረጋል። እንዲወር የተላከውም የመናመቀጠዋ ወረዳ ነበር። ለወረራ የዘመተው ወታደር ቀለቡንም ሆነ ምኝታውን የሚያገኝው በወረራ ከያዘው ማህበረስብ ስለነበር ለዚህም ሲባል  በየአለቃው እየሆነ በየመንደሩ ይሰማራል። በዚህም ወረራ የከምከም ቃሮዳ ህዝብ ክፉኛ መጎዳቱ የታወቃል።ይህም ፊውዳላዊ የማስገበሪያ ዘዴ በሁሉም አካባቢ ሲተገበር የኖረ እንጂ የህወሃት ተላላኪዎች እንደሚሉት የወልቃይትን ማህበረሰብ ሆን በሎ ለማጥቃት የተደረገ አንድም ወረራ አልነበረም።

ይልቁንም ፀሃፊው ተወልደው ባደጉበት አካባቢ የልጅነትና የወጣትነት ዘመን ላይ የተፈጸመን ተመሳሳይ እውነተኛ ታሪክ ፍጹም አጣሞና አዛብቶ ለህወሃት ሴራ በሚመች መልኩ ማቅረብ፤ አንድም ህወሃት ማኒፌስቶ ቀርፆና አካባቢውን በሃይል ተቆጣጥሮ የወልቃይት ጠገዴን ዘር አፅድቶ በትግሪያዊነት ለመተካት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የትግራይ ሰፋሪዎች በማስፈር የተጓዘበትን  ዘግናኝ የዘር ማፅዳት ወንጃል በስመ “ወረራ” ለማቃለልና ለማድበስበስ የታለመ ሲሆን በሌላ መልኩ ደግሞ  ህወሃት በአማራ ህዝብ ላይ በቀጣይነት ለሚፈጽመው የዘር ማጽዳት ፍጅት መንገድ ጠራጊ ሆነው ለማገልገል ቆርጠው መነሳታቸውንና በአማራ ህዝብ ላይ ሊያካሂዱ ያቀዱትን ግጭት በፊታውራሪነት ለመምራት የሄዱበትን እርቀት ያመላክታል።

  1. አቶ ሃይሉ “ምዝበራው አልበቃ ብሎ አባወራውን አባርረው ሚስቲቱ አስገድዶ መድፈር የተለመደ ነበር” ይላሉ።

“የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም” እንዲሉ እዚህ ላይ እነ አቶ ሃይሉ የሺወንድም ቀስ በቀስ የገቡበት ህወሃታዊ የክህደትና የሸፍጥ ቁልቁልት ጥልቅና መውጫ ወደሌለው እንጦሮጦስነት ሲቀየር እናያለን።

የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ እንኳንስ በሚስቱና በዕርስቱ ለመጣበት ይቅርና በዋዛ በፈዛዛ ክብሩን ለነካ ሁሉ ምላሹ ጥይት እንደሆነ ጠላታችን ህወሃት ሳይቀር ጠንቅቆ ያውቃል። ይህን በታሪካችን ተሰምቶም ሆነ ታይቶ የማያውቅ ፀያፍ ምግባር በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ላይ እንደተፈጸመ አድርጎ ማቅረብ በቅድሚያ ከሁሉም በላይ ይህ ለሆዱ ያደረ ተንበርካኪ ስብስብ ለወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ያላችውን ንቀት የሚያሳይ ሲሆን፤ በመቀጠልም ድርጊቱን ፈጽሟል ብለው በሚከሱት የጎንደር-አማራ ህዝብ ላይ ያላቸውን ከልክ ያለፈ ጥላቻ ምን ድረስ ሊጓዝ እንደሚችል በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው።

ለመሆኑ የትኛው ወልቃይቴ ወይም ጠገድቼ ነው ከወራሪ ወታደር የተወለደና አባቱን የማያውቅ? የትኛውስ አባወራ ነው ሚስቱን አስደፍሮ በማህበረሰቡ ውስጥ ተዋርዶ የኖረው? ከዚህ ከተዋረደ ቤተሰብ ውስጥ የተወለዱ ልጆች እነማን ናቸው? የልጅ ለጆቹስ እነማን ይሆኑ? እንግዲህ መልሱን ለእነ አቶ ሃይሉ የሺወንድም እንተዋለን።

እኛ ግን እንዲህ እንላለን። ይህን በታሪካችን ተሰምቶም ሆነ ታይቶ የማያውቅ ፀያፍ ምግባር በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ላይ እንደተፈጸመ አድርጎ ማቅረብና ማስተጋባት የማንም ሳይሆን ዕርስታችንን በወረራ ይዞ ዘራችንን እያጥፋና አካባቢያችንን በትግሪያዊነት እየተካ የሚገኘው ህወሃት በህዝባችን ላይ ያለውን ንቀትና ጥላቻ ያሳየበት ሲሆን እስከዛሬ በህዝባችን ላይ በዝግ ለፈፀማቸውና ነገ ታሪክ ለሚያወጣቸው ግፎችና ፀያፍ ድርጊቶች ፍንጭ የሰጠበት መንገድ ነው እንላለን።

እንዲህም እንመሰክራለን። ከህወሃት በፊት በነበሩ ስርዓቶች ሁሉ እንዲህ አይነት ፀያፍ ድርጊት በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ላይ አይደለም ሊፈፀም ይቅርና በወሬ ደረጃ ተሰምቶም እንደማያውቅ ምስክሮች ነን። ይህ የፈጠራ ክስ ህወሃት የወልቃይት ጠገዴን ማህበረሰብ ክብር ለማዋረድና አኩሪ ታሪኩን ለማንቋሸሽ የሄደበት ፀያፍ መንገድ ነው።

2ሴራ፡  የወልቃይት ጠገዴን ከአማራዊነት መነጠል

  1. ውንጀላ እና የሃሰት ምስክርነት

ፀሃፊው በመጣጥፋቸው እጅግ አደገኛ የሆኑ ሁለት የፈጠራ ውንጃላዎችን በማቅረብ የሃሰት ምስክርነታቸውን ይሰጣሉ።

1ኛ. በስደት የሚገኙት የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆች በአሁኑ ሰዓት በሀገር የተቀጣጠለውና የአማራ ምንነት እንቅስቃሴ የሚመሩ ወገኖችን አጀንዳውን ያገኙት የተሰጣቸው ከዲያስፖራው ነው የሚል ሲሆን፤

2ኛ. “የወልቃይት አማራ ማንነት እንቅስቃሴ በአጭር ጊዜ ተደማጭነት ያገኘው … የብአዴንን ቡራኬ ስላገኘ ” በማለት የወገናችንን የዘመናት ትግልና መስዋዕትነት ውጤት የሆነውን ይህን ታላቅ ድል እራሱን እንኳ ከህወሃት ቁንጥጫ ማዳን ለማይቻለው የብአዴን ባርኮት ያደርጉታል።

እነዚህ ሁለት ውንጀላዎች ህወሃት ከመጀመሪያው ጀምሮ የሚያላዝንባቸውና አሁንም ወገኖቻችንን ለማሸማቀቅና እንደለመደው አፍኖ ለማጥፋት የሚያደርገው ቅድመ ሁኔታ ነው። በተለይም በአለፉት የእንቅስቃሴው የመጀመሪያ ወቅቶች የነበረው ህወሃት ሌላውን ተላላኪውን አቶ ፈረደ የሺወንድምን ወደ ጐንደር በመላክ የእንቅስቃሴውን የኮሚቴ አባላት ለማስፈራራት መሞከሩ የሚታውቅ ሲሆን በእንቅስቃሴው አመራር አባላት መካከል አንዳችም አይነት ጉዳት ቢደርስ ተጠያቂ የሚሆነው አቶ ፈረደ እና ግብረ አበሮቹ እንደሆኑ የኮሚቴው አባላት ለቤተሰቦቻቸው መናገራቸውን ልብ ይሏል።

አሁንም ይህ ተመሳሳይ ውንጅላ በአቶ ኃይሉ የሺወንድም መደገሙ “አያ ጅቦ ሳታማኽኝ ብላኝ” ያለችው እንሰሳ ታሪክ ያስታውሰናል። ስለሆነም በኮሚቴው አባላት ላይና  የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ጥያቄ! ፊርማ ማስባሰቢያ ሰነድ ላይ በፈረሙ የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆች ላይ የሚደረሰው ማንኛውም ህወሃታዊ አፈና እና ጥቃት ግንባር ቀደም ተጠያቂ የሚሆኑት በመግቢያችን እንደገለፅነው በዋናነት ወ/ሮ አዜብ መስፍን፣ አቶ ፈረደ የሺወንድም፣ አቶ ሃይሉ የሺወንድም፣ አቶ ፀጋዬ አስማማው እና የጥቅም ታጋሪዎቻቸው መሆናቸውን ከወዲሁ ልናረጋግጥ እንወዳለን።

  1. ወልቃይትን ከጠገዴ መነጠል

ቡድኑ በመጣጥፉ በገፅ 5, 2ኛው አንቀጽ ላይ “ወረራውና ዘመቻው እንደ ባህል ሆኖ፣ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በጠገዴው ተወላጅ በክቡር ቢትወደድ አዳነ መኮንን አስተዳደር ሳይቀር በየምክንያቱ ተመሳሳይ ዘመቻዎች ተካሂደዋል። የቢትወደድ ቀብቲያ ላይ በጥይት መቁሰልና የጀግናው ወጣት አርበኛ ወልቃይቴ የመኮነን በርሄ (ጎንደሬ በጋሻውን ያንብቡ) መገደል ከዚህ አይነቱ ዘመቻ ጋር የተያያዘ ነበር።” ይለናል።

በክቡር ቢትወደድ አዳነ መኮንን የአስተዳደር ዘመን በወልቃይት ላይ የተፈጸመው ወረራ ከላይ በሰፊው እንደገለፅነው የፊውዳሉ ስርአት አንድን ለስርአቱ አልገዛ ወይም አልገብር ያለን ወረዳ ወይም አንገዛም ያሉ ግለሰቦች (ሽፍቶች)  ለመቅጣትና ለማስገበር ይጠቀምበት የነበረው አይነተኛ ዘዴ ሌላውን አጎራባች ወረዳ እንዲዘምትበትና እንዲወረው ብሎም እንዲያስገብረው የማድረግ አንዱ አካል ነው። ከዚህም በመነሳት በዘመኑ በወልቃይት ማህበረሰብ እንደ ጀግና በፊውዳሉ ስራአት ደግሞ እንደ አመፀኛ ይቆጠር የነበረው ወጣቱ አርበኛ መኮነን በርሄን ለመያዝና ለመንግስት ለማስረከብ የታዘዘው የክቡርነታቸው አስተዳደር ነበር።

ይሁን እንጂ ክቡር ቢትወደድ አዳነ መኮንን ምንም እንኳ በመንግስት መኮነን በርሄን ይዘው እንዲያቀርቡ ቢታዘዙም ወደ ወልቃይት ጦር አላዘመቱም። ይልቁንም እራሳችው ከጥቂት ወታደሮቻቸው ጋር ወደ አካባቢው በመሄድ የወልቃይትን ፊታውራሪዎች በማማከር  በሽምግልና ምህረት ተደርጎለት እንዲገባ ይስማማሉ። መኮነን በርሄንም እኛ ዋስ እንሆንሃለን በማለት የእራሱ ዘመዶች ፊታውራሪዎቹ ክቡር ቢትወደድ አዳነ መኮንን ዘንድ ይዘውት ይቀርባሉ። እሳቸውም አባታዊ ምክራቸውን ለግሰው ዋስ እንዲጠራ ይጠይቁታል። እርሱም በሽምግልና ያመጡትን ፊታውራሪዎች ለዋስትና ቢጠይቅ ከወንድሞቹ አንድም የሚዋሰው ሰው ያጣል። በዚህም ጊዜ በሽምግልና ባመጡት ዘመዶቹ ክህደት የተናደደው ጀግና መታሰሬም ሆነ መሞቴ አይቅርልኝም በሚል ደብቆ በያዘው ሽጉጥ ክቡር ቢትወደድ አዳነ መኮንን ያቆስላል። በወቅቱም ቢትወደድ ከወደቁበት ሆነው እንዳትገሉት በማለት ያስጠነቀቁ እንደነበርና ነገር ግን እዛው የነበሩት ሁሉ ተረባርበው እንደገደሉት ታሪክ ህያው ምስክር ነው።

እውነታው ይህ ሆኖ እያለ ሆን ተብሎ ታሪክን በማጣመም በጠገዴ ተወላጆች አማካኝነት በወልቃይት ማህበረሰብ ላይ የተፈፀመ ወረራ አድርጎ ማቅረብ ይልቁም አንድ አካል አንድ አምሳል ከሆነው የጠገዴ ህዝብ የተገኙት ጀግናው አባታችን ክቡር ቢትወደድ አዳነ መኮንን ሆን ብለው ወልቃይትን ለመበቀል የዘመቱና በወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ዘንድ እንደ ጠላት ወይም በዳይ እንደሚቆጠሩ ተደርጐ መቅረቡ እጅግ የተሳሰተና ከእውነታውም የወጣ ነው። እርግጥ ነው ክቡር ቢትወደድ አዳነ መኮንን ወደ ወልቃይት የዘመቱበት ጊዜ አለ። ይኸውም ለጣሊያን ባንዳ ሆነው አገር የከዱትን ደጃዝማች ለመያዝና ለመቅጣት እንደነበር ታሪክ በደማቁ ፅፎታል።

ከዚህም በመነሳት ቀደም ሲልም ፀሃፊው “በህዝቦች መካከል ሰላም ለማውረድና አላስፈላጊ ቁርሾን ለትውልድ ላለማስተላለፍ” በማለት ስለትግራይና ወልቃይት ህዝብ ፍቅርና ሰላም የተጨነቁትና የተጠነቀቁትን ያህል በዚህኛው የፅሁፋቸው ክፍል በጠገዴና በወልቃይት ማህበረሰብ መካከል ምን አይነት ፍቅርና አንድነት ለመገንባት እንዳሰቡና እንደጣሩ ከወዲሁ መመልከት ይቻላል።

በመጀመሪያ አንድ የታሪክ ማስረጃ እናቅርብ። ጣሊያን ኢትዮጵያን ለቆ በወጣ ማግስት የስሜን አውራጃ ህዝብ ጣሊያን ባደረሰበት ግፍና መከራ የተነሳ እጅግ በከፋ ድህነት ውስጥ እንደሚገኝና እንደሚሰቃይ፤ የዘመኑንም ግብር የመክፈል አቅም እንደሌለውና ምህረት እንዲደረግለት ለአፄ ኅይለስላሴ መንግስት ጥያቄ ያቀርባሉ። ነገር ግን ጥያቄውን ያልተቀበለው የአፄ ኅይለስላሴ መንግስት የስሜን አውራጃ በሰላም እንዲገብርና ፈቃደኛ ካልሆነ በሃይል እንዲገብር ትእዛዝ ይተላለፋል። ይህንም እንዲያስፈፅም ከመንግስት የታዘዘው የክቡር ቢትወደድ አዳነ መኮንን አስተዳደር ነበር። እንደተለመደው የክቡር ቢትወደድ አዳነ መኮንን ጦር ፊታውራሪ አጥናፉ መሸሻ የሚገኙበትን የስሜን አውራጃን ለመቅጣትና ለማስገበር ይዘምታል። በዚህም ጦርነት የቢትወደድ አዳነ መኮንን ጦር ይሸነፍና ቢትወደድ አዳነም ቆስለው ይማረካሉ። ይሁን እንጂ ፊታውራሪ አጥናፉ መሸሻ የዘመቱባቸውን ቢትወደድ አዳነን በክብር ተቀብለውና ይቅርታ ጠይቀው፣ የራሳቸውን በቅሎ በመስጠት ወደ መጡበት መልሰዋቸዋል።

ከዚህ ታሪካዊ እውነታ የምንረዳው ነገር ቢኖር ከላይ እንዳየነው ወደ ወልቃይት የዘመቱት አማራው የጠገዴው ተወላጅ ክቡር ቢትወደድ አዳነ መኮንንና ጦራቸው ወደ ሌላኛው አማራ ወደሆነው የእነ ፊታውራሪ አጥናፉ መሸሻ የስሜን አውራጃ ግዛት ለማስገበር በማእከላዊው መንግስት ትእዛዝ መዝመቱን እንረዳለን። ይህም ድርጊት በመላው ኢትዮጵያ ሲሰራበት የነበረ አሰራር ነበር።

ከእነዚህ የታሪክ እውነታዎች በመነሳትና “በህዝቦች መካከል ሰላም ለማውረድና አላስፈላጊ ቁርሾን ለትውልድ ላለማስተላለፍ” በማለት ስለትግራይና ወልቃይት ህዝብ ፍቅርና ሰላም የተጨነቁትና የተጠነቀቁትን በማየት የእነ አቶ ኃይሉ የሺወንድም በክቡር ቢትወደድ አዳነ መኮንን ጦርና በጠገዴ ላይ ያቀረቡት ውንጀላና ክስ ስንመለከት አላማው ግልፅ ይሆናል። ይኸውም ወልቃይትና ጠገዴ የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ መሆናቸው አይደለም የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ወራሪው ጣሊያንም ያውቀዋል።

ነገር ግን አንድ የጠገዴን ህዝብ ከሁለት በመክፈል ግማሹን ወደ ጎንደር/አማራ ሌላውን ግማሽ ደግሞ ወደ ትግራይ በመከለል ሁለት ጠገዴ የፈጠረው ተስፋፊውና ወራሪው የትግራይ ነፃ አውጭ ቡድን ከጠገዴ ማህበረሰብ በኩል የደረሰበትን “አንድ ጠገዴ እንጂ ሁለት ጠገዴ የለም!” የሚለውን የህዝብ ተቃውሞ ለማፈንና በወልቃይት ማህበረሰብ ከተቀጣጠለው የወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ! ጋር የተፈጠረው የትግል አንድነትና ትብብር ለማዳከምና ነጥሎ ለማጥቃት ሲል ህወሃት በተላላኪዎቹ በኩል የከፈተው የመከፋፈል ዘመቻ አካል መሆኑን ወገናችን ጠንቅቆ ይረዳል።

የሆድ – አደሮቹ አጀንዳ

  1. “የወልቃይት አማራ ማንነት ኮሚቴ አባላትና ደጋፊዎቻቸው ከተመደበላቸው ስራ ጎን ለጎን ለስታተስ ኮ አንቲ ቅድመ ሁኔታ መሳካት ትርጉም ያለው ጥረት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።” በማለት ከ 7 ገፅ በላይ በመፃፍ ለከሰሱትና ለወነጀሉት ታጋይ ህዝብና ኮሚቴ የራሳቸውን አጀንዳ ሊጭኑበት ይሞክራሉ።

የዚህ አጀንዳ ምንጩና አላማው አንድና አንድ ነው። ይኸውም በወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ላይ ከ37 ዓመታት በላይ የተፈፀመው ዘርን የማፅዳትና አካባቢውን በትግሪያዊነት የመተካት ወንጀል በዓለም አደባባይ መጋለጡ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎናችን መቆሙና፣ ይልቁንም ህዝባችን በጎንደርና በመላው የአማራ ህዝብ ደጋፍና ትብብር ታሪካዊ የተባለለትን ህዝባዊ ጥያቄ አንግቦ በአንድነት መነሳቱ ህወሃት በሃይል የወሰደውን የጎንደር ለም መሬት እንዲመልስ የሚይስገድድ ከሆነ፤ በስመ ምርጫ በሃይል የወረረውን ወልቃይት ጠገዴን ህጋዊ አድርጎ ለመጠቅለል የታለመ ቀጣይ ሴራ እንደሆነ እንረዳለን።

እኛ የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ማንነታችንን በሚመለከት “ህዝበ ውሳኔ” የምንሰጥበት መነሻም ሆነ መድረሻ ምክንያትና ግብ የለንም፡፡ ሊኖረንም አይችልም፡፡ መፍትሄውም እጅግ በጣም ቀላልና ግልፅ ነው፡፡ ይኸውም መሬታችንና ማንነታችን ከ1983 ዓ.ም በፊት ወደነበረበት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይመለስ፡፡ አራት ነጥብ!!!

  1. ህወሃት ዛሬ በተላላኪዎቹ በኩል “የትግራይ ሰፋሪዎችን ከወልቃይት ጠገዴ ማስወጣት” እያለ የሚያናፍሰው ወሬና የሚዘራው መርዝ፤ ትላንት በተመሳሳይ መልኩ ጠፍጥፎ በሰራቸው ተላላኪዎቹ አማካኝነት አባቶቻችን ውድ ህይወታቸውን ሰውተው በክብር ባቆዩልን ሃገራችን ውስጥ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆችን ለዘመናት ከኖሩባቸውና ጎጆ መስርተው፣ ልጆች ወልደው አሳድገውና ድረው፣ ሃብትና፣ ንብረት አፍርተው በሰላም ከሚኖሩባቸው የኦሮሚያ፣ የቤንሻጉል፣ የጋምቤላና፣ የደቡብ ክልሎች በጀምላ እንዲባረሩና ሜዳ ላይ እንዲወድቁ የተደረገበትን በእጅጉ ያሳዘነንና ያስቆጣንን እኩይ ድርጊት በትግራይ ተወላጆች ላይ እንዲደገም የታለመ ሴራ እንደሆነ ጠንቅቀን እናውቃለን። ይልቁንም “በህዝቦች መካከል ሰላም ለማውረድና አላስፈላጊ ቁርሾን ለትውልድ ላለማስተላለፍ” በማለት የተመፃደቁበትና ለህዝቦች ሰላምና ለትውልድ አርቆ አሳቢ ለመምሰል የሞከሩበት ብዕራቸው ነጥፎ “የትግራይ ሰፋሪዎችን ከወልቃይት ማስወጣት” በማለት በህዝቦች መካከል የማይበርድ እሳት ሲጭሩ እንመለከታለን።

እኛ ግን ከዚህ ቀደምም ባወጣናቸውና ለህዝብ ይፋ ባደረግናቸው ሰነዶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ደጋግመን በግልፅ እንዳስቀመጥነው ሁሉ ዛሬም በድጋሚ አቋማችንን እንደሚከተለው አቅርበናል።

ኢትዮጵያ ሃገራችን ሁሉም ኢትዮጵያውያን በሰላም፣ በፍቅር፣ በመከባበር፣ በእኩልነትና፣ በአንድነት የሚኖሩባት የጋራ ቤታችን ናት! መሆን አለባት የሚል ፅኑ እምነት አለን። ማንኛውም ኢትዮጵያዊ/ት በማንኛውም የኢትዮጵያ ክፍል በነፃነት ተንቀሳቅሶና የዜግነት መብቱ ያለአንዳች ገደብ ተከብሮለት፤ በሰላም ሰርቶ ሃብት የማፍራት፣ ጎጆ መስርቶ የመኖርና፣ ለጆች ወልዶ የማሳደግ ፍፁም እኩል መብት አለው፤ ሊኖረውም ይገባል የሚለው የቀደምት አባቶቻችን ኢትዮጵያዊ መርሆ ለወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ ከትውልድ ትውልድ ሲተላለፍ የኖረና እኛም በተግባር የኖርንበት ኢትዮጵያዊ ማንነታችንና እንደ አንገት ማተባችን የምንጠብቅው ቃልኪዳናችን ነው። ለዚህም ተቀዳሚው ምስክራችን የትግራይ ህዝብ ነው።

ስለሆነም ማንኛውም በህወሃት ሴራም ሆነ የሃሰት ፕሮፖጋንዳ ተወናብዶ ወይም ሰርቶ ለመኖርና ልጅ ወልዶ ለማሳደግ ወደ ወልቃይት ጠገዴ በህወሃት የሰፈራ ዕቅድ ምክንያት የሰፈረ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ እንደ ቀድሞው ሁሉ የወልቃይት ጠገዴን የጎንደር-አማራ ብሄርተኝነትና አስተዳደር ተቀብሎ እስከኖረ ድረስ የዜግነት መብቱ ሙሉ በሙሉ ተከብሮለት ሊኖር ይገባል ይሚል ፅኑ እምነትና አቋም አለን። ለዚህም መብት መከበር አበክረን እንሰራለን።

ማጠቃለያ

እራሱን የትግራይ ነፃ አውጭ እያለ የሚጠራው ፀረ-ኢትዮጵያ፣ ፀረ-ሰላም ቡድን ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ በወረራ በያዘቸው የጎንደር ታሪካዊ መሬቶች ላይ በሚኖሩ የወልቃይት ጠገዴና የጠለምት አማራ ተወላጆች ላይ ያደረሰው የዘር ማፅዳትና በትግሪያዊነት የመተካት ዓለም-አቀፍ ወንጀል በአስቸኳይ እንዲቆምና አፋጣኝ የመፍትሄ እርምጃዎች እንዲወሰዱ የሁሉንም ሰላም ወዳድ የሰው ዘር ድጋፍ የምንሻበት ሁኔታ ውስጥ እንገኛለን። በተለይም ላለፉት 37 ዓመታት የህወሃትን ህገ-ወጥ መስፋፋትና ወረራ ለመግታት በሁሉም አቅጣጫ ሲታገል የኖረው ህዝባችን፤ ዛሬም ያለውን ሃይል በማሰባሰብና ትግሉን በወጣት ልጆቹ በማጠናከር ከፍተኛ መሰዋዕትነት እየከፈለ ይገኛል።

በአንፃሩ ህወሃት ዛሬም ቢሆን በስግብግብነት የያዝውን በአያት ቅድመ-አያቶቻችንን ክቡር አፅም የተዋጀችውን ዕርስታችንን በሰላማዊ መንገድ ላለመልቀቅ እንደቆረጠ የሚያሳዩ ተጨባጭ መረጃዎች ይታያሉ። በተለይም የህወሃት  የ2 ዜግነት ጥቅማጥቅም ያንበረከከው  ቡድን አማካኝነት ታጋዩን ህዝባችን ለመከፋፈልና ለማዳከም ሲል ብቻ ጋምቤላውያንን ከመሬታቸው በሃይል በማፈናቀል ለነዚህ ሆዳሞች በገፍ እያከፋፈለና የሃገሪቷን ገንዘብ ሳይቀር እየረጨላቸው እንደሚገኝ በተጨባጭ መስረጃ ለማረጋገጥ ችለናል።

ይሁን እንጂ ይህ ከወራሪው የጣሊያን መንግስት የተቀዳ ህወሃታዊ ሴራ እጅግ ያረጀና ያፈጀ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም ወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ጠንቅቆ የሚያውቀው በመሆኑ ህዝባችን አንድነቱንና ፅናቱን ጠብቆ፣ ለሆድ አደሮች የማደናገሪያ ጩኸትና፣ የማዘናጊያ ድርድሮች ጆሮውን ሳይሰጥ፤ ያነገበውን የወልቃይት ጠግዴና ጠለምት የአማራ ማንነት ጥያቄ! ከግቡ ሳያደርስና፣ የጀመረውን ዘሩን የማዳንና የአባቶቹን ዕርስት የማስመለስ ትግል በድል ሳያጠናቅቅ እንደማይመለስ ፅኑ እምነታችን ነው።

በመጨረሻም የወልቃይት ጠግዴና ጠለምት የአማራ ማንነት ጥያቄ! በውስጡ የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎችና የመዳረሻ መፍትሄዎች ያካትታል።

1ኛ. ወደ ቀደመው የጎንደር ግዛት መመለስ

ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ታሪካዊና መልክዓምድራዊ አካላችን ወደሆነው ጎንደር/የበጌምድር ግዛታችን መመለስ! ይህም ማለት ማንኛውንም መሰረታዊ የማንነታችን መገለጫዎች የሆኑትንና በተለይም ባህላችንና ቋንቋችን በነፃነትና ያለምንም ገደብ መጠቀም ወደምንችልበት ሁኔታ መመለስን ያካትታል፡፡ እነርሱም፡-  በክልላችን ውስጥ በሚካተቱ በማንኛውም መንግስታዊም ሆኑ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፤ እንዲሁም በትምህርት ቤቶች አማርኛ ቋንቋችን የመጠቀም መብታችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መከበር፣ ታሪካዊ መጠሪያ ስማቸው ተቀይሮ በትግሪያዊ ስሞች የተተኩትን ት/ቤቶች፣ መንገዶችና፣ የአካባቢዎች ወደ ቀደመ ይዞታቸው መመለስና የመሳሰሉትን ጉዳዮች ያካትታል።

2ኛ. ዕርስት ለባለ ዕርስቱ

የተፈናቀሉትና የተሰደዱት የአካባቢው ተወላጆች ወደ ዕርስታቸውና ቀያቸው በመመለስ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የርስታቸው ባለቤት ማድረግ፡፡ ከስደት ተመላሹ ወገናችን ከዜሮ የሚጀምረውን ታሪካዊ ኑሮ ብዙ የሚባልላቸው ጉድለቶች እንደሚያጋጥሙትና በጊዜ ሂደት ሊሟሉ የሚችሉ የመሆናቸው ነገር እርግጥ ቢሆንም መሰረታዊ የሆኑት የማህበራዊ ህይዎት ግብአቶች እንዲሟሉለትና አካባቢው ሰላምና መረጋጋት ሰፍኖበት ኑዋሪዎቹም ያለስጋት ሰላማዊ የዕለት ከዕለት ቀጣይ ኑሮዋቸውን በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲያከናውኑ ማስቻል ያስፈልጋል።

3ኛ. ወንጀለኞችን ለፍርድ ማቅረብ

አካባቢችን ከፍተኛ ወንጀል የሚፈፀምበትና እስከ አሁንም ድረስ ለማንኛውም ገለልተኛ አካላት ዝግ ነው። በተለይም መንግስታዊ ላልሆኑ የሃገር ውስጥና የውጭ ሃገር ድርጅቶች፣ ለጋዜጠኞች፣ ለሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በአካባቢው መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም አካባቢው  ለማንኛውም ገለልተኛ አካል ምርመራና እይታ ክፍት እንዲሆን በማድረግ የህወሃት አፈናና ወጥመዱ ተሰብሮ የወገናችን በደልና ስቃይ ለዓለም ሰላም ወዳድ ህዝቦች እንዲደርስ በማስቻል፣ የተፈፀመው ወንጀል በገለልኛና ነፃ አካላት እንዲጣራ በማድረግ ወንጀለኞቹን ለፍርድ ማቅረብ የግድ ይሆናል፡፡ በዚህም ለዘመናት የፈሰሰው የወገናችን እንባ ይታበሳል፤ ዓለማችንም ለወንጀለኞ ማምለጫ ቦታ እንደማይኖራት ይረጋገጣል።

4ኛ. የትግራይ ሰፋሪዎችን መልሶ ማቋቋም

በህወሃት የትግሪያናይዜሽን እኩይ ወጥመድ ተጠልፈው በወለቃይት ጠገዴና ጠለምት አካባቢዎች ሰላማዊና የተደላደለ ኑሮ መኖር የጀመሩትን የትግራይ ሰፋሪዎች ደህንነታቸውና ምቾታቸው ተጠብቆ ይኖሩ ዘንድ መርዳትና ማስቻል። ይኸውም እነዚህ ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ ከትግራይ አካባቢዎች በተለያየ መንገድ መጥተው በዕርስታችን የሰፈሩት የትግራይ ሰፋሪዎች እንደፍላጎታቸው ወደ ትግራይ የመመለስ ድጋፍ ሊደረግላቸው ይገባል እንላለን፡፡

በመጨረሻም

ይህ ወቅታዊና ታሪካዊ ሰነድ እንዲዘጋጅ ከጅምሩ ግፊት ያደረጉ፣ በአዘጋጅነት ተመድበው የሰሩ፣ እጅግ ጠቃሚና አስፈላጊ የታሪክ ማስረጃዎችንና ሰነዶችን ያደረሱንና፣ በአጠቃላይ ሙሉ ድጋፋቸውን በመስጠት ከጎናችን ላልተለዩን በሃገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ወገኖቻችን ላቅ ያለ ምስጋናችን ይድረሳችሁ።

በሌላ በኩል በጉዳዩ ያገባናል ያሉ አያሌ ምሁራንና ድርጅቶች የህወሃትንና የተላላኪዎቹን ሴራ ለማጋለጥና ትክክለኛውን ታሪካዊ እውነታ ለኢትዮጵያውያን ለማድረስ ያዘጋጇቸውን ሰነዶች ለጊዜው እንዲያዘገዩልን በጠየቅናቸው መሰረት መልካም ፈቃዳቸውንና ቀና ትብብራቸውን ቸረውናልና ላቅ ያለ ምስጋናችን ይድረስልን።

ይልቁንም የህወሃትና ግፍና ጭካኔ ለወገንና ለዓለም ህብረተሰብ ለማጋለጥ በምናደርገው ትግል ከጎናችን ለተሰለፋችሁና መልእክቶቻችን በወቅቱ ለሚመለከተው ሁሉ ላደረሳችሁልን ድህረገጾች፣ ጋዜጣዎች፣ ሬዲዮኖችና ቴሌቪዥኖች ባጠቃላይ የህዝብ መገናኛ አውታሮች ሁሉ ከፍ ያለው ምስጋናችንና አክብሮታችን ይድረሳችሁ፡፡

ማንኛውንም አስትያየት፣ መርጃ፣ ወይም ጥያቄ በሚከተለው አድራሻ ለአዘጋጆቹ ሊያደርሱን ይችላሉ።

አባይ መንግስቱ፣ ቻላቸው ዓባይ፤ ጐሹ ገብሩና፣ አብዩ በለው

aamg50@yahoo.com

ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!

ድል ለህዝባችን!

ጥር 19፣ 2008 ዓ.ም

The post ወልቃይት ጠገዴ ማነው? appeared first on Zehabesha Amharic.

አማራ አለ ወይስ የለም?

$
0
0

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ወያኔና ሌሎች የጥፋት ኃይሎች አማራን የማጥፋት የቆረጠ የጥፋት ዓላማና ድርጊት ይዘው መምጣታቸውና ሀገሪቱን ከመቆጣጠራቸው የወሰዱት የተቀናጀ ዘግናኝ የዘር ማጥፋት ጥቃት መፈጸማቸው የአማራ ልኂቃንን አስጨንቆ ሕዝቡን ከወያኔና መሰሎቹ የዘር ማጥፋት ጥቃት የታደጉ፣ የሠወሩ፣ ያዳኑ፣ የከለሉ፣ የተከላከሉ መስሏቸው ሁለት የተለያዩ አቋሞችን ለማራመድ ሲያስገድድ ከአማራው ሕዝብም ቀላል ቁጥር ያልያዘውን ምናልባትም አሁን የአማራ ሕዝብ ተብሎ ከሚገለጸው የሚበዛውን በተለይ በወያኔ አጠራር የአማራ ክልል ተብሎ ከሚጠራው ውጭ ርቆ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያለውን አማራ ነኝ ብሎ ያምን የነበረውን ዜጋም ማንነቱን እንዲቀይር የያለበትን አካባቢ ብሔረሰብ ነኝ ብሎ ማንነቱን እንዲክድ አስገድዷል፡፡ ወያኔ ኦሮሚያ ብሎ ከሚጠራው የሀገራችን ክፍል ብቻ ከ7 እስከ 10 ሚሊዮን (አእላፋት) አማሮች ጥቃትን በመፍራትና ከጥቃት ለመዳን በማሰብ ማንነታቸውን ወደ ኦሮሞነት ለውጠው ኦሮሞ አድርገዋል፡፡

amhara

አስገራሚው ነገር ይሄ አይደለም እዛው ወያኔ የአማራ ክልል ብሎ ከሚጠራው የሀገራችን ክፍል ያለው አማራም በዘሩ የተቀላቀለችውን የሌላ ብሔር በተለይም የትግሬን እያሰላ አማራነቱን የካደና ትግሬ ነኝ ያለ መኖሩና አማራ ነኝ የሚለውም ወያኔ ለአማራ ያለውን ስር የሰደደ ጥላቻና የማጥፋት ዓላማ እንዳለው እያወቀም ከወያኔ ጋር ተሰልፎ ይሄንን የወያኔን የጥፋት ዓላማ የሚፈጽምና የሚያስፈጽም መኖሩ ነው፡፡ እነኝህን ግለሰቦች በብዛት “ብአዴን” ተብሎ በሚጠራው የወያኔ አሻንጉሊት ውስጥ ታጉረው ታገኟቸዋላቹህ፡፡ አማራን ይዘልፋሉ ከወያኔ በሚቀበሉት ትእዛዝ ባሕሉን ማንነቱን ታሪኩን አጠቃላይ እሴቶቹን ያጠፋሉ የተለያየ ጥቃት ያደርሳሉ፡፡

 

ከላይ የጠቀስኳቸው ሁለቱ የልኂቃን ቡድኖች ደግሞ አንደኛው “አማራ የሚባል ብሔረሰብ የለም!” የሚለው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ “ከዚህ የዘር ማጥፋት ጥቃት መትረፍ የምንፈልግ ከሆነ በቅናትም ይሁን በሌላ ምክንያት ለመጠቃት ምክንያት የሆኑብንን ማንነታችንን፣ እሴቶቻችንን፣ ትውፊታዊ ሀብቶቻችንን፣ ቅርሶቻችንን፣ መለያዎቻችንን፣ ኩራቶቻችንን፣ መብቶቻችንን፣ የሥልጣኔ ፍሬዎቻችንን ወዘተረፈ. አሳልፎ መስጠት፣ መተው፣ መጣል፣ መሠዋት፣ የእኛ መሆኑን አለመጠየቅ አለመናገር አለመመስከር፣ እንደሚገደን እንደሚያገባን አለመናገር፣ አንገታችንን አቀርቅረን መቀመጥ፣ የፈለጉትን ቢያደርጉት ዝም ማለት” ብለው የሚያምኑና ይሄንንም በማድረግ ከሌሎቹ ጋር ለመግባባት የሚሞክሩ ከወያኔና ከሌሎች የጥፋት ኃይሎች ጋር ሳይቀር ተባብረው የሚሠሩና ለመሥራት የሚጥሩ ከሀዲያን ናቸው፡፡

 

“አማራ የሚባል ሕዝብ ወይም ብሔረሰብ የለም!” የሚሉቱ ከመጨነቃቸው የተነሣ ለበጎ አስበው ይሄንን ነገር ቢያደርጉትም ይሄ ድርጊት ወያኔ በአማራ ሕዝብ ላይ እያደረሰበት ካለው የዘር ማጥፋት ወንጀል ባልተናነሰ የከፋና የከበደ አደጋ እንዳለው በወቅቱ ያሰቡት አይመስለኝም፡፡ ይሁን እንጅ እንዳልኩት ይሄንን የሚሉ ወገኖች ስለጨነቃቸው እንጅ በእርግጥም “አማራ የሚባል ብሔረሰብ የለም!” ብለው ስለሚያምኑ ነው ይሄንን ያሉት ብሎ ማለት የዋህነት ነው፡፡ ይህ አባባል ጉዳት ያለው ቢሆንም እነሱ ለክፉ አስበው ስላላደረጉት ሊዘለፉ የሚገባም አይመስለኝም፡፡

 

እንዳጋጣሚ ሆኖ ይሄንን አመለካከታቸውን ሕዝቡ አልተቀበለውም እንጅ ተቀባይነት አግኝቶ “አማራ የለም!” በሚለው አስተሳሰብ ቢሠራበት ኖሮ ለዚህች ሀገር የጀርባ አጥንት ሆኖ ስንት መሥዋዕትነት የከፈለ ስንት ታሪክ የሠራ ሕዝብ እንዳልነበረ ሆኖ ጠፍቶ ተረስቶ ቀርቶ ነበር፡፡ የተባለው ነገር የዚህን ያህል ጉዳት ባያደርስም ግን ይህ “አማራ የለም!” የሚለው አባባል እራሳቸውን ከጥቃት ለማዳን ማንነታቸውን የካዱትን የአማራ ተወላጆችን እንዲህ ዓይነቱን ክህደት በራሳቸው ላይ እንዲወስዱ ተጨማሪ ምክንያት ሳይሆን እንዳልቀረ መገመት ይቻላል፡፡ ለአንድ ሕዝብ ከዚህ በላይ ኪሳራና ጉዳት ምንም ነገር ያለ አይመስለኝም፡፡ “የለም!” በመባሉ ጨርሶ የመረሳት የመፋቅ አደጋ ባይደርስበትም አለ በመባሉ ከወያኔ ይደርስበታል ተብሎ ከተፈራው አደጋ የከፋ አደጋና አደገኛ ውጤት በተለያየ መልኩ እየደረሰበት ይገኛል፡፡

 

ሲጀመር ወያኔ አማራ አለ ብሎ አምኖ በራሱ እምነት “አማራ” ያለውን ወገን እየመነጠረ ለማጥፋት ቆርጦ እስከተነሣና ይሄንንም ተግቶ እስከፈጸመ ጊዜ ድረስ እኛ “አማራ የለም!” ማለታችን ማንነታችንን በገዛ ራሳችን በመካዳችን ለወያኔ ድርብ ድል ይሰጠው እንደሆን ነው እንጅ “የለም!” በማለት ወያኔ የዘመተበትን ሕዝብ ከጥፋት ለመከላከል የማይረዳ መሆኑን አለመገንዘብ የዋህነት፣ እጅ መስጠት፣ ጥቃት ወይም ሽንፈትም ነው፡፡

 

የወያኔ ችግር አማራ ተብሎ የሚጠራ ሕዝብ መኖሩ እንጅ ያ ሕዝብ አማራ መባሉ ላይ አይደለም፡፡ አማራ አማራ መባሉ ቀርቶ ሌላ ሥያሜም ቢኖረው ኖሮ አማራ ስላልተባለ ከወያኔና መሰሎቹ ጥቃት የሚያድነው አይደለም፡፡ ስለሆነም አባባሉ ጭንቀት የወለደው እንጅ ታስቦበት የተባለና እውነትም ሆኖ የተባለ አይደለም፡፡

 

እዚሁ ላይ አንድ ግራ የሚገባኝ ነገር ቢኖር “አማራ የለም!” ብለው የሚሉ ወገኖች እራሳቸውን ማን ብለው ነው እየገለጹ ያሉት? ሌላ ብሔረሰብ እየጠሩ ወይስ ብሔረሰብ የሌለኝ ኢትዮጵያዊ ነኝ እያሉ? ይህ አባባል ስሕተት የሚሆነው አማራ ብቻ የለም በመባሉ ነው እንጅ ሌሎቹም የሉም ቢባል ስሕተት ባልሆነ ነበር፡፡ ምክንያቱን “ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ከጥፋት የሚታደገው ብቸኛው መንገድ!” ከሚለው ጽሑፍ ላይ ይመልከቱ፡፡

 

ወያኔና ሌሎች የጥፋት ኃይሎች አማራን ለማጥፋት የተነሡት የጥፋት ኃይሎች እንደሚያወሩትና የዋሀን የአማራ ተወላጆችና ሌሎችም እንደሚመስላቸው አማራ ግፍ ስለፈጸመ አይደለም ልብ በሉ ይሄንን ስል በሌሎች ሀገራት እንደተፈጸሙት ያለ ግፍ በሀገራችን አልተፈጸመም አልኩ እንጅ የዚህ ወይም የዚያ ዘር ብሔረሰብ አባል በመሆን መናቅ መገፋት አልነበረም እያልኩ አይደለም፡፡ ይሄም ቢሆን ግን “እዬዬም ሲዳላ ነው” እያልን ካልሆነ በስተቀር ይህ ጉዳይ ተጋኖ ጭራሽም ለፖለቲካዊ (ለእምነተ አሥተዳደራዊ) ፍጆታ ውሎ በሀገርና በሕዝብ ህልውናና ደኅንነት ላይ አደጋ እስኪጋርጥ ድረስ ትኩረትና ቦታ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ በፍጹም በፍጹም አልነበረም፡፡ ይሄ አለመብሰል ነው፡፡ ምክንያቱም አንዳች ነገርን ምክንያት በማድረግ መናናቅ ያለ የነበረና የሚኖር ሊጠፋም የማይችል በመሆኑ ነው፡፡ የሰው ልጆች ሰው በመሆናችን ካሉብንና ከውስጣችን ልናጠፋቸው ከማንችላቸው ደካማ ጎኖች ይሄ አንዱ በመሆኑ፡፡

 

በእርግጠኝነት የምነግራቹህ ነገር ቢኖር “ኦሮሞ በመሆናችን ትግሬ በመሆናችን ወዘተረፈ. እንናቅ እንገፋ ነበር” የሚሉ ፖለቲከኞች (እምነተ አሥተዳደራዊያን) እንዲያው ሌላውን ሁሉ ነገር ተውና እነሱ ዛሬ ከተሜ ሆነው ከተሜነትን እያጣጣሙ ስለሆነ ብቻ በገጠር ዘመዶቻቸው በወንድም በእኅቶቻቸው በእናት በአባቶቻቸው የሚያፍሩ የሚሸማቀቁ ከእነሱ ጋር አብሮ መታየትን የማይፈቅዱ፤ አካለ ስንኩል ወይም የአእምሮ ዘገምተኛ የቤተሰብ አባል ካለም እንዲያ የሆነው ሰው ለተጎዳው ያንን ችግርም በራሱ ላይ ያመጣው ራሱ ተጎጅው ፈልጎ ያመጣው ይመስል ከባድ የሆነ ንቀት ጥላቻ ማግለል ችግሩ ባለበት የቤተሰባቸው አባል ላይ የሚፈጽሙ የእነሱ የቤተሰብ አባል መሆኑም እንዲታወቅ የማይፈልጉ አብረው ለመታየት በፍጹም የማይፈቅዱ ናቸው፡፡ ይሄ የእነሱ ችግር ብቻ ነው እያልኩ አይደለም ይህ ችግር እንደሌለባቸው ሁሉ በመመጻደቃቸው ችግሩ የእነሱም እንደሆነ ለማሳየት እንጅ፡፡

 

እንግዲህ ይሄ የሚያመለክተው አንዳች ነገርን ምክንያት አድርጎ መናናቅ ተፈጥሯዊ የሆነ ሰው የመሆን ደካማ ጎን መሆኑን ነው፡፡ ይህ ተፈጥሯዊ ደካማነትም ተፈጥሯዊ እንደመሆኑ ሳንፈልግና ሳንፈቅድም ተገደን በሁሉም ማኅበራዊ ጉዳዮቻችን ላይ ይንጸባረቅብናል፡፡ ቆንጆ እኅት እራሷን እንደዛ አስውባ የፈጠረችው እሷው እንዳልሆነች እያወቀችም በፉንጋ እኅቷ ታፍራለች ትሸማቀቃለች እኅቷ መሆኗንም መናገር አትፈልግም አብራ መታየት ያሸማቅቃታል ባስ ሲልም እኅቷ መሆኗን ትክዳለች፡፡ እንዲህ እንዲህ እያልን ለመናቅ የሚያበቁ ምክንያቶች ሌላው ቀርቶ የአንድ ቤተሰብ አባላትን እንኳን ያስተዛዝባል ግንኙነት ያሻክራል መለያየትን ይፈጥራል፡፡

 

እንግዲህ ይህ ችግር ድንቁርና የሚሆነው ተፈጥሯዊ መሆኑን ካለመገንዘብና እኛው እራሳችንም በሌላ መልክ በገዛ ቤተሰባችንም የምንፈጽመው በደልና ግፍ መሆኑን ካለመረዳት በአንድ ብሔረሰብ ውስጥ ባሉ ጎሳዎች መሀከል እራሱም አንደኛው በሌላኛው ላይ የሚፈጽመው በደል መሆኑንና የተለየ ነገር እንዳልሆነ ልብ ካለማለት ትግሬ፣ ኦሮሞ ምንትስ በመሆናችን ተናቅን ተገፋን በማለት ለፖለቲካዊ (ለእምነት አሥተዳደራዊ) ጉዳይ ፍጆታ ለማዋል የተነሣን እንደሆነ ነው ለማንም የማይጠቅም ተግባርና ከድንቁርናም ድንቁርና የሚሆነው፡፡ ምክንያቱም ተራው አማራ እራሱም በመሳፍንቱና በመኳንንቱ የተናቀ የተገፋ ለጋብቻ ለዝምድና የማይፈለግ የማይመረጥ የተጠላ የተረገጠ የተጨቆነ ነበርና፡፡

 

እንዲህ ስል ዘርን ምክንያት አድርጎ የሚፈጸም የመናቅና መገፋት በደል ትክክል ነው ይቀጥል እያልኩ አይደለም ምክንያት እየፈጠሩ መናናቅ ተፈጥሯዊ ቢሆንም በተቻለ መጠንም እንዲቀር መሥራትማ ይገባል፡፡ እኔ እያልኩ ያለሁት ችግሩ ሁላችንም የምንፈጽመው ተፈጥሯዊ ችግር ነውና ተፈጽሞ ስናይ አይግረመን ለመጥፎ ዓላማም አንጠቀምበት ነው እያልኩ ያለሁት፡፡ ይሄም በመሆኑ ነው ጥቁርም የሰው ልጅ ሆኖ ሳለ ጥቁር በመሆኑ ብቻ ምንም በደል ሳይኖርበት እስከዛሬም ድረስ የሥልጣኔ ጣራ ላይ ደርሰዋል አዋቂዎች ናቸው በምንላቸው በነጮቹ ግፍና በደል እየተፈጸመበት የሚገኘው፡፡ ጥቁሩ ጥቁር ስለሆነም ብቻ አይደለም በነጮቹም መሀከል እርስ በእርሳቸው አንዱ የዚህ ወይም የዚያ ዘር በመሆኑ ብቻ አንዱ ሌላውን ይንቀዋል ያገለዋል ወዘተረፈ…

 

እና ችግሩ እንዲወገድ መሥራቱ የሚገባ ቢሆንም ቀርፈን በማንቀርፈው ነገር ላይ ለመጥፎ ዓላማ በመጠቀም ጊዜያችንን ገንዘባችንን ሁሉን ነገራችንን ማባከን ኪሳራን እንጅ ትርፍን አያመጣም እንዲያውም ይሄ ችግር ሲነኩት ይብስ እብደሚገማ እንደሚገን አንዳች ነገር በመሆኑ የዚህ መድኃኒቱ ንቆ መተዉና ትኩረት ባለመስጠት እንዲረሳ ለማድረግ ቢጣር ነው የተሻለ የሚሆነው፡፡ ንቀን የተውነው እንደሆነ ነው በሁለንተናችን ላይ ችግር የመፍጠር አቅም የሚያጣው፡፡

 

ወደቀደመው ነገራችን እንመለስና ወያኔ በአማራ ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል ለመፈጸም ታጥቆ ተነሥቶ በግልጽና በስውር ይሄንን ሰይጣናዊ ተግባር እየፈጸመ ያለው በሌሎች ከእኛ ጋራ ተመሳሳይ የመንግሥት አሥተዳደር በተበራቸው ሀገራት ዘርን መሠረት አድርጎ የተፈጸመው ዓይነት ግፍ በደል በትግሬነቱ የተፈጸመበት ኖሮ ያንን ለመበቀል ሳይሆን “አሜን ብሎ የማይገዛልኝና የማይተኛልኝ ቀን ጠብቆ የሚበቀለኝ አማራ ነው!” ብሎ ስለሚያስብ፣ በዚህች ሀገር ላይ በብቸኝነት ነግሦ ለመኖር ካለው አንባገነናዊ ዓላማው አንጻር እና ከበረሀ ጀምሮ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ጠላት ከሆኑ ባዕዳን ከተሰጠው አማራን የማጥፋት ተልዕኮውና ዓላማው የተነሣ ነው፡፡ ስለሆነም “አማራ የለም!” በማለት አማራን ከወያኔ ሰይጣናዊ ጥቃት ልንታደገው አንችልም፡፡

 

ከዚህ ቀደም ደጋግሜ እንዳነሣሁት ኦሮምኛ በመናገራቸውና “የኦሮሞ” የሚባልን ባሕልና እሴት በመከተላቸው ኦሮሞ ነን እንደሚሉትና እንደተባሉት፤ የትግሬ የጉራጌ ወዘተረፈ. የሚባልን ቋንቋ ባሕልና እሴት በመከተላቸው ትግሬ ነን፣ ጉራጌ ነን ወዘተረፈ. እንደሚሉትና እንደተባሉት ሁሉ አማርኛ በመናገራቸው የአማራ የሚባልን ባሕልና እሴት የሚከተሉ እያሉ “አማራ ሊባሉ አይገባም አማራ የለም!” ማለት እጅግ የተሳሳተ አስተሳሰብ ነው፡፡ ሲጀመር ጎሳ ብሔረሰብ ነገድ ሐሳባዊ እንደመሆኑ በዚህ መለኪያ ከሔድን አማራ ብቻ ሳይሆን ሁሉም የለም፡፡ ምክንያቱም አማራም እንደሌሎቹ የሰው ዘሮች ሁሉ የተገኘው ከአዳም ወይም ከሉሲ ስለሆነ አማራ በመሆኑ በተፈጥሮው ከሌሎቹ የተለየ አይደለምና፡፡

 

የጎሳ የብሔረሰብ የነገድ ህላዌ ሐሳባዊ የሚሆነው በዚህ ምክንያት ነው፡፡ እያንዳንዱ ጎሳ ነገድ ብሔረሰብ ከተለያዩ አዳሞች ወይም ሉሲዎች የመጡ ባለመሆናቸው፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ በእርግጠኝነት ጠልቆ ለመረመረ ሰውና የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ኩነት ለሚያውቅ እያንዳንዱ ሰው ቢያንስ ከሦስት ቢበዛ ደግሞ ካምስትና ከዚያ በላይ የተለያዩ ብሔረሰቦችና ጎሳዎች ያልተወለደ ዜጋ የለምና የሕዝቡ ስብጥራና ደም እንዲህ የተዋሐደ በሆነበት ሁኔታ ከማንም ጎሳ ወይም ብሔረሰብ ያልተዋለዱ ያልተዋሐዱ የራሳቸው የብቻቸው አዳም ወይም ሉሲ ያላቸው አባላት ያሉት ብሔረሰብ ወይም ጎሳ ፈጽሞ በሌለበት ሁኔታ ትግሬ ኦሮሞ ወዘተረፈ. ብሔረሰብ ወይም ጎሳ ሊኖር ስለማይችል ከነዚህ ከነዚህ አንጻር አማራ ብቻ ሳይሆን ሌሎቹም የሉም ሊባል ይችላል፡፡

 

ከዚህ በመለስ ግን ሳይንሳዊም ባይሆን በዘልማድ እየሠራንበት ነውና ኦሮምኛ ቋንቋ  ቋንቋችን ነው ብለው ኦሮምኛ በመናገራቸው የኦሮሞ የተባለን ባሕልና እሴት በመከተላቸው ኦሮሞ የሚባሉ ከሆነ አማርኛ ቋንቋ ቋንቋችን ነው ብለው የአማራ የተባለን ባሕልና እሴት የሚከተሉት አማራ መባል አይገባቸውም የሚል ካለ ይሄ ሲበዛ የዋህና የማያስተውል ነው፡፡

 

ወደ ኋላም ዐየን ወደ ፊት የአንድን ብሔረሰብ አባላት እንዲህ የሚባሉ ብሔረሰብ ናቸው ለማለት እየተሠራበት ያለው መሥፈርት ቋንቋና ባሕል ከሆነ ይህ መሥፈርት አማራ ላይ ሊሠራ የማይችልበት ምንክያት ምንድን ነው? ብሔረሰቦች የሚፈጠሩት በጊዜ ሒደት አንደኛው ከነበረው እየወጣ የራሱን ቋንቋና ባሕል አዳብሮ ሲገኝ ነው እንጅ ከሆኑ የተለያዩ ቦታዎች ከተለያየ ምንጭ ተፈጥረው መጥተው ቁጭ ቁጭ ያሉ ኅብረተሰባዊ ቡድኖች አይደሉም፡፡ ሁሉም የተቀዱትና የወጡት ከአንድ የሰው ዘር ምንጭ ነው፡፡

 

ወደ ሁለተኛው ቡድን ማለትም “አማራ በአማራነቱ ብቻ መጠቃቱ የጨነቃቸውና አማራ ከዚህ ጥቃት መትረፍ የሚፈልግ ከሆነ በቅናትም ይሁን በሌላ ምክንያት ለመጠቃት ምክንያት የሆኑበትን ማንነቱን፣ እሴቶቹን፣ ትውፊታዊ ሀብቱን፣ ቅርሱን፣ መለያውን፣ ኩራቱን፣ የሥልጣኔ ፍሬውን ወዘተረፈ. መተው፣ መጣል፣ አሳልፎ መስጠት፣ መሠዋት ወይም የእሱ መሆኑን አለመናገር አለመመስከር እንዲጠፉ መፍቀድ አለበት” ብለው ወደሚያምኑትና ይሄንንም በማድረግ ከሌሎቹ ጋር ለመግባባት ወደ ሚሞክሩትና ከዚያም አልፈው ከወያኔና ከሌሎችም የጥፋት ኃይሎች ጋር ተባብረው ወደሚሠሩት ጅሎች፣ ራስ ወዳዶች፣ ፈሪዎች፣ ከሀዲዎችን ስናይ ከእነዚህ ሰዎች አብዛኞቹ በአንደበታቸው እንዲህ ብለው ሲናገሩ አትሰሟቸውም ይሄንን ብለው እንደሚያስቡና እንደሚያምኑ የምታውቁት በድርጊቶቻቸው ነው፡፡

 

ከአማራ ውጪ የሆነ ደካማ ዜጋ እንዲህ ብሎ ቢያስብ ቢሠራም ባልገረመኝ አማራ ሆነውና የአማራ ልኂቃን ሆነው እንዲህ የሚያስቡ የሚያደርጉም ዜጎች መኖራቸው ነው እኔን በእጅጉ የሚደንቀኝ፡፡ አማራ ከሌላው የተለየ ፍጥረት ነው ሌላው ከአማራ ያነሰ ነው ማለቴ ሳይሆን አማራ የሆነው የራሱ ለሆነው እሴት ሊገደው ሊቆረቁረው ሊቆጭ ባለአደራነት ሊሰማው ሲገባው ይሄንን ሳያደርግ መቅረቱ በእጅጉ ቢገርመኝ ነው፡፡

 

መቸስ ወያኔ የተሳካለት ነገር ቢኖር ኢትዮጵያዊያንን ከዳር እስከ ዳር የነበረንን ብሔራዊ መግባባት ድብልቅልቁን ማውጣቱ ደብዛውን ማጥፋቱና በታሪክ በባሕል በማንነት እሴቶቻችን ላይ ልዩነትና አለመግባባት ፈጥረን የኢትዮጵያ የሆነው ሁሉ የአማራ ብቻ እንደሆነ እንዲቆጠር በማድረግ የማንም እንዳይሆን አማራ ነን በሚሉት ሳይቀር የጥፋት ዘመቻ እንዲዘመትበት ማድረጉ ላይ ነው፡፡

 

እጅግ የሚገርመኝ ነገር ቢኖር የጥፋት ኃይሎቹ የሚያደርጉትና ጥያቄያቸውን ፍትሐዊና ትክክለኛ እንዳይሆን የሚያደርገው “የኢትዮጵያ ይሄ ብቻ አይደለም (የአማራ ብለው የሚያስቡት) ሌላም አለ እሱ ይጨመር ማለት ሲገባቸው በጥቅሉ ይሄ የነበረው አይደለም እሱ መጥፋት አለበት ይሄ እኛ የምንለው ነው መሆን ያለበት” በማለት ከባድ የጥፋት ዘመቻ ማድረጋቸው ነው፡፡ ይሄ እንግዲህ የተበደልን የተገፋን ነን ብለው እራሳቸውን ከሚገልጹት ወገኖች በኩል ያለው አተያይና አስተሳሰብ ድርጊትም ነው፡፡

 

ጨቋኝ ገዥ ከተባለው ወገን የሆነውና ታደርሱብን ትፈጽሙብን ነበር ተብሎ እንደተነገረው “የተፈጸመባቸውን ግፍ በደልና መገፋት መገንዘብ መረዳት አለብኝ” ብሎ የሚያስበው ተራማጅ ነኝ ባይ የወያኔ የኦነግና የሌሎች የጥፋት ኃይሎች የጥፋት ሥራቸው ተባባሪዎች ከሀዲያኑ ለዚህ ስሕተት የዳረጋቸው ነገር ቢኖር ስለራሳቸው ስለታሪካቸው ምንም የሚያውቁት ነገር የሌለ መሆኑና በወያኔና በሌሎች የጥፋት ኃይሎች የሚወራው የተቀነባበረ የፈጠራ ስም ማጥፋት እውነት መስሎ የሚታያቸው መሆኑ ነው፡፡

 

እንዲህ በማሰባቸው ነው ከሀዲያኑን ከወያኔና ከሌሎቹም የጥፋት ኃይሎች ጋር አብሮ በመቆምና በመሰለፍ የአማራ ተብሎ በተፈረጀው በኢትዮጵያ ታሪክ ባሕልና የማንነት እሴቶች ላይ በጥፋት አብረው እንዲዘምቱ እንዲተባበሩ የሚያደርጋቸው፡፡ አሁን አሁን እግጅ አስደንጋጭ በሆነ ሁኔታ ቀድሞ የምናደንቃቸው በተቃውሞው ጎራ ያሉ አንዳንድ የአማራ ልኂቃን ሳይቀሩ የዚህ ወያኔ የፈጠረው ምልከታ ሰለባ ሆነው የወያኔና የኦነጋዊያን የጥፋት ሥራና የጥፋት ዓላማ ተባባሪ ሆነው እያየን ያለንበት ዘመን ላይ ደርሰናል፡፡ እነኝህን ዓይነት ወገኖችን ወያኔን ለመታገል ቆርጠው በተሰለፉ ቡድኖችና ድርጅቶችም ጭምር ታገኟቸዋላቹህ፡፡

 

ይህ ውድቀትና አደጋ አሳሳቢ ከመሆኑ የተነሣ ችግሩን ከስሩ ማየትና እነኝህ ወገኖችን ያሳሳተውን ብዥታ ማጥራትና ወደ ትክክለኛው አስተሳሰብ ማምጣት አስተላጊ ሆነ በመገኘቱ ይሄ ጽሑፍ ተጽፏል፡፡ ስለሆነም በዚህ ጽሑፍ ላይ፡-

• አማራ እንዲህ እንዲህ አድርጓል እየተባለ በወያኔና በሌሎች የጥፋት ኃይሎች አማራ እንዲጠላ እየተነዛ ያለው ሁሉ ወሬስ እውነት ትክክል ነው ወይስ ሐሰት?

• ለመሆኑ አማራ እንደ ሕዝብ በዳይ፣ ገፊ፣ ጨቋኝ ሆኖ ያውቃል? ወይስ ተበዳይ፣ ተገፊ፣ ተጨቋኝ?

• እስከአሁን የኢትዮጵያ ተብሎ የሚገለጸው ታሪክ ባሕል እሴቶች የማንነት መለያዎች ሁሉስ የጥፋት ኃይሎች እንደሚሉት እውን የአማራ ብቻ ነው ወይ?

• የአማራ የሆኑትስ አማራ ኢትዮጵያዊ እንደመሆኑ የኢትዮጵያ ሀብት ሆነው መቆጠር መጠበቅ ይኖርበታል እንጅ የአማራ ስለሆነ ይጥፋ ተብሎ ሊፈረድበት የሚችልበት የሕግ የፍትሕ አግባብ አለ ወይ?

• የፍትሕ የእኩልለት ጥያቄ አለን በማለት የእኛም ታሪክ ባሕል እሴቶች ይታወቅ ይመዝገብ ይዘከር የሚሉ ወገኖችስ የአማራ የሚሉት እንዲጠፋ እንዲወገድ እንዳይታሰብ እንዳይዘከር ቦታ እንዳያገኝ ለማድረግ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ለሀገርና ለሕዝብ ህልውና እድገት ሥልጣኔ ጠቃሚ ወይስ አጥፊ፣ መፍትሔ ሰጪ ወይስ ተጨማሪ ችግር ፈጣሪ?

• ሀገሪቱ ብሔር ብሔረሰቦች ባሕላቸውን፣ ሥልጣኔያቸውን፣ እሴቶቻቸውን ወዘተረፈ. በእኩል ዕድል ማቅረብ የሚችሉባት ሚዛናዊ መድረክና መስተንግዶ የሚያገኙባት ሀገር መሆን አለባት ሲባልስ ምን ማለት ነው? ትክክለኛና አመክንዮአዊስ ነው ወይ?

እነኝህንና ተያያዥ ነጥቦችን በጥልቀት እናያለን፡፡ ከርእሰ ጉዳዩ ግዝፈት አንጻር ጽሑፉ ረዘም ብሏል ለዚህ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡

እነዚህ ወገኖች ይሄንን በማድረጋቸው ሀገርንና ወገንን ከጥፋት ለመታደግ የሚያስችል ሁነኛ አኪያሔድ መስሎ ይታያቸዋል፡፡ በእርግጠኝነት ልነግራቸው የምፈልገው ነገር ቢኖር ኢፍትሐዊና አግባብ ያልሆነን ጥያቄ በመቀበልና በማስተናገድ የሚገኝ ሰላምና ደኅንነት ሊኖር የማይችል መሆኑን ነው፡፡ ሰላምና ደኅንነት በፍትሐዊና ትክክለኛ መሠረት ላይ ካልተመሠረተ የሚገኘው ሰላም አስተማማኝና ዘላቂ አይሆንም፡፡ እውነትን ለድርድር ማቅረብ ትርፉ ኪሳራ እንጅ መልካም ሊሆን አይችልም፡፡ ለሀገርም ለወገንም ዘላቂና አስተማማኝ ሰላምና ደኅንነት እንዲመጣ ከተፈለገ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለእውነት ለአመክንዮ ለእፍትሕ ታማኝ ሆኖ ክብርና ዋጋ ሰጥቶ መቅረብ ግዴታው ነው፡፡

ዳኛው ታሪክ ነው፡፡ ታሪክ እንደየ ሥራችን ይፈርደናል፡፡ ችግሩ የጥፋት ኃይሎች ዳኛው ታሪክ ከሆነ የጥፋት ዓላማቸው ፍላጎታቸውና ማግኘት የሚፈልጉትን ኢፍትሐዊ ጥቅም ማግኘት እንደማይችሉ አውቀው የሀገርን ታሪክ በመቶ ዓመታት መገደባቸውና ከዚያ በፊት ያለውን በዓይን የሚታይ በእጅ የሚዳሰስ ቅርስ አሻራ ማስረጃና መረጃ ያለውን የሀገሪቱን ታሪክ ሁሉ ተረት ተረት የፈጠራ ወሬ ነው ብለው አቋም መያዛቸውና አንቀበልም ማለታቸው ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ለአመክንዮ ለሞራል (ለቅስም) ለፍትሕ መገዛት በእነዚህ እሴቶች መዳኘት ፈጽሞ ከማይፈልግ አካል ጋር ተግባብቸና ተስማምቸ እሠራለሁ ብሎ ማሰብ እጅግ ቂልነትና ከባድ ዋጋም የሚያስከፍል ስሕተት ነው፡፡

ያለን አማራጭ በጥፋት ዓላማና ፍላጎት ሰክረው የናወዙትን እነኝህን አካላት ወደ ትክክለኛው ተቀባይነት ወዳለው አስተሳሰብ እንዲመጡ ሳይታክቱ ለማግባባት መጣር ነው፡፡ ይህ የማይሆን የማይረዱ የማይገባቸው ከሆኑና አልሆን ካለ ግን ቆርጦና ጨክኖ መፋለም ብቻና ብቻ ነው ለው አማራጭ እንጅ ኢፍትሐዊ ኢአመክንዮአዊ ኢሞራላዊ ጥያቄዎቻቸውን ተቀብሎ ማስተናገዱ አይደለም መፍትሔው ምክንያቱም እንዳልኳቹህ ስሕተት በመሥራት የሚመጣ ሰላምና ደኅንነት የለምና ሰላምና ደኅንነት በአለት ላይ ሲመሠረት እንጅ በድቡሽት ላይ ሲመሠረት ዘላቂ ሊሆን አይችልምና፡፡

ይሄንን ማስጠንቀቂያ ተላልፎ ኢፍትሐዊ ኢአመክንዮአዊ ኢሞራላዊ ኢሰብአዊ ጥያቄዎች ካሏቸው ወገኖች ጋር በነገሮች በቂ ግንዛቤና እውቀት ካለመያዝ በጥፋት ኃይሎች የሚወራው ትክክለኛ እውነት እንደሆነ በመገመት ከእነሱ ጋር የሚሠራ ለሀገርና ለወገን ተቆርቀዋሪ የሚመስለው ወገን ካለ በሀገርና በወገን ላይ የሚያደርሰው ጥፋት ወያኔና ሌሎቹም የጥፋት ኃይሎች ካደረሱትና ከሚያደርሱት ልተለየ የማይሆን መሆኑን አጥብቄ ማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡ ምክንያቱም ሰላምና ደኅንነት ከጥፋት ኃይል ጋር በመሥራት ስለማይመጣ ሰላም በአለት መሠረትላይ እንጅ በድቡሽት ላይ ተመሥርቶ ዘላቂና አስተማማኝ ስለማይሆን፡፡

እነኝህ ወገኖች ስንሰማቸው አንባገነንነትን ጭቆናን አፈናን ተቃዋሚ ታጋይ ኮናኝ ነን እያሉ ሀገርና ሕዝቧ ዕድሜ ዘመናቸውን የፈጁበትን ስንትና ስንት የተደከመበትን የሀገርና የሕዝብ ሥልጣኔ ፍሬ የሆኑትን እሴቶች የጠላት ንብረት አድርገው የአማራ ነው ሊበለጽግ ሊያድግ ሊስፋፋ አይደለም በጭራሽ ልናየው አንፈልግም በማለት ለማጥፋት ወገባቸውን አስረው ሲሠሩ አንባገነንነትን ጭቆናን አፈናን እንቃወማለን እንታገላለን ባዮቹ እነሱ እራሳቸው የወጣላቸው አንባገነን ጨቋኝ አፋኝ አጥፊ እንደሆኑ መገንዘብ የሚችል ጭንቅላት ያላቸው ቡድኖች አይደሉም፡፡

ይሄንን መገንዘብ መረዳት የተሳናቸው ወይም የማይፈልጉ የኢሞራላዊ፣ የኢፍትሐዊ፣ የኢሰብአዊ፣ የኢአመክንዮአዊ አስተሳሰብናና አግባብነት የሌለው በቀል የተሞና ሰብእና ያላቸው አካላት ከዚህ የደነቆረና አጥፊ አስተሳሰባቸው ካልተፈወሱ በስተቀር በምንም መመዘኛ ቢታዩ ለሀገርና ለየትኛውም ሕዝብ የሚጠቅሙ የሚበጁ አይደሉም፡፡ እንኳንና ለሌላ ለየግላቸውም የሚበጁ አይደሉም፡፡ ለዚህም ነው ሀገርንና ወገንን የጠቀሙ መስሏቸው ከአጥፊ አስተሳሰባቸው ሳይለወጡ ለመለወጥም ሳይፈልጉ ከነአጥፊ አስተሳሰባቸው ከነሱ ጋር ተባብሮ ለመሥራት የሚሞክሩ ወገኖችን በእርግጠኝነት አብረዋቸው በመሥራታቸው የሚፈልጉትን ውጤት ማምጣት አይችሉም ያልኩት፡፡

የወያኔና እንደ ኦሕዴድ ደሕዴግ ወዘተረፈ. ያሉ የወያኔ አሻንጉሊት ድርጅቶች፣ የኦነግና የሌሎች የጥፋት ኃይሎች ጥፋት ምንድን ነው?

ይህ ጥፋት አማራን “ጠላትና መጥፋት ያለበት!” ብለው ከመደምደማቸው የሚመነጭ የጥፋት ተግባር ነው፡፡ የሚያደርሱትንም ከባባድ የጥፋት ተግባር ለመደገፍ በአማራ ላይ ከባባድ የሆኑ የፈጠራ ክሶችንና የስም ማጥፋቶችን በማናፈስ የጥፋት ተግባራቸውን ለመደገፍ ጥረት ያደርጋሉ፡፡ ከጥፋቶቹ ጥቂቶቹ፡-

የኢትዮጵያ ታሪክ ተብሎ ያለው ታሪክ የአማራ ታሪክ ነው፡፡ እሱም ቢሆን ፈጠራ ነው ተረት ተረት ነው ይወገድ ይጥፋ ተብሎ በ18 (አሁን ጨምሮ ሊሆን ይችላል) ዩኒቨርስቲዎች (መካነ ትምህርቶች) የታሪክ ትምህርት እንዲዘጋ ማድረጋቸው፣ “የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ነው” በሚል የደነቆረ ሽፋን የሀገር (እነሱ የአማራ ይሉታል) እሴቶች የነበራቸውን ቦታ እንዲያጡ ብሎም እንዲጠፉ ማድረጋቸው፡፡ ለምሳሌ አማርኛ ዛሬ ብሔራዊ ቋንቋ አይደለም የሥራ ቋንቋ ነው ብለዋል የሥራ ቋንቋ እንደመሆኑ ግን እንደ የሥራ ቋንቋነቱ የመጠናት የመመርመር የመበልጸግ መብቱን ነፍገው በየዩኒቨርስቲው (መካነ ጥምህርቱ) ቀድሞ የነበሩትን የአማርኛን ሥነጽሑፍ ማዕከል ያደረጉ ክፍለ ጥናቶችን (ዲፓርትመንቶችን) እንዲዘጉ ማድረጋቸው ዋና ዋና ዎቹ ናቸው፡፡

እርግጥ ነው የኢትዮጵያ ታሪክ ተብሎ ሆን ተብሎ የሌሎቹ ተዘንግቶ የአንድ ዘር ብቻ እንዲጻፍ ተደርጎ ቢሆን ኖሮ በጣም ስሕተት ነበር፡፡ የሚገርመው ግን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በየትኛውም ቦታ የተጻፈ የሀገራችን ታሪክ አንዱም ቢሆን “የአማራ ታሪክ ነው” ተብሎ የተጻፈ አለመሆኑ ነው፡፡ እስኪ የሩቁን ትተን የቅርቡን የአድዋን ድል እንይ መቸና የትስ ነው የአድዋ ድል የአማራ ታሪክ ነው ተብሎ የሚያውቀው? በዚህ ታሪክ ላይ የሌሎች ብሔረሰቦች ጉልህ ድርሻ አልተጻፈም ወይ? እኒህንና መሰል ጥያቄዎችን እያነሣን ስንጠይቅ የጥፋት ኃይሎቹ የጥፋት ሥራ አግባብነት ከሌለው ጥፋቻ ብቻ የመነጨ እንጅ ተጨባጭነት ያለው ሆኖ አይገኝም፡፡

እርግጥ በታሪክ ላይ አንድ ዓለማቀፋዊ እውነታ አለ፡፡ ሁሌም ታሪክ የሚጻፈው ለገዥዎች ባደላ መልኩ ነው፡፡ ሰፊውን ቦታም የሚይዘው የእነሱ ሕይዎት እንጅ የዝቅተኛው ኅብረተሰብ ክፍል ሕይዎት አይደለም፡፡ ይሕም ቢሆን በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ በወቅቱ የነበረው ኅብረተሰብ ሕይዎት መጠቀሱ አይቀርምና ገዥዎቹም ቢሆኑ ኢትዮጵያዊያን ናቸውና እንዴት ሆኖ የኢትዮጵያ ሊባል አይገባም ይጥፋ ሊባል እንደሚችል አይገባኝም፡፡ “የዝቅተኛውን ኅብረተሰብ ሕይዎት ያዘለ አይደለምና የተሟላ አይደለም” አንድ ነገር ነው የነበረው የየወቅቱ ዝቅተኛ ኅብረተሰብ ሕይዎት ካለና የሚታወቅ ከሆነ እሱን አምጥቶ ማሟላትም የሚያስመሰግን ተግባር ነው፡፡ እንዲያው ግን በደፈናው የገዥውን ክፍል ብቻ ነውና የሚያወራው የኢትዮጵያ ታሪክ ሊባል አይገባል እንዴት ሊባል ይችላል? የማን እንበለው ታዲያ? ኢትዮጵያዊያን አይደሉም ወይ? ኢትዮጵያዊያን እንደመሆናቸው ያለው ታሪክ በቂ በሚባል ደረጃ የዝቅተኛውን ኅብረተሰብ ክፍል ሕይዎት የያዘ የገለጸ አለመሆኑ እንዳለ ሆኖ እንዴት ነው የኢትዮጵያ ሊሆን ሊባል የማይችለው? የተሟላ አለመሆኑ ይገለጻል እንጅ እንዴት የኢትዮጵያ አይደለም ሊባል ይችላል? ይሄስ ችግር ዓለማቀፋዊ አይደለም ወይ? ታሪክ ሁሌም የሚጻፈው በአሸናፊዎች እንደመሆኑ አድልኦ ግነትና ውስንነት ቋሚ የታሪክ ሰነዶች ችግሮች አይደሉም ወይ? ይሄ በመሆኑ እንደእናንተ ሁሉ የሀገራችን ታሪክ አይደለም ብሎ ታሪኩን የጣለ ያጠፋ እንዲጠፋ የሚሠራ የሠራ ሀገር ማን አለ? እስኪ ጥቀሱልን?

መቸም በአንዲት ሀገር ላይ ደናቁርት ሥልጣንን ሲቆጣጠሩ አደጋው ይሄው ነው፡፡ በዚያች ሀገር የሚያደርሱት ጥፋት ሊነገር ከሚችለው በላይ ነው፡፡ በኛም ሀገር ላይ የሚታየው ይሄው ነው፡፡

ታሪክ ማለት በሀገሪቱ ያሉ የሁሉንም ብሔረሰቦች እሴቶች “እኩል” ስፍራ ሰጥቶ ማስተናገድ እንደሚጠበቅበት የብሔረሰቦች ሙዚየም (ቤተ መዘክር) ማለት አይደለም፡፡ በቤተ መዘክር እንኳን እራሱ በመርሕ ደረጃ እኩል ስፍራ ይባላል እንጅ ይሄንን አሠራር ተግባራዊ ማድረግ የሚቻልበት ሁኔታ በየትም ሀገር የለም፡፡ ቅንነት ከማጣት ሳይሆን ካለው ተፈጥሯዊ ገዥ ሕግ አኳያ እንጅ፡፡ ምክንያቱም አንደኛው በርካታ የበለጸጉ የታሪክ የባሕል የመሳሰሉት ቅርሶችና መገለጫዎች እሴቶች ሲኖሩት ሌላኛው ደግሞ የሌላኛውን ያህል የሌለው ይሆናልና፡፡

እናም “የሀገር ታሪክን ድርሻ ለየብሔረሰቡ እኩል እናከፋፍላለን!” ማለት አባባሉ ቀናና ፍትሐዊ ቢመስልም አላዋቂነት የተጫነው ቂልነትና ነባራዊውን ሀቅ ያልተገነዘበ አስተሳሰብ ነው፡፡ ሲጀመር ጀምሮ ዓለም የኢፍትሐዊነት መድረክ ናት፤ የአሸናፊዎች ሀብት ናት፡፡ ታሪክ የሚባለውም ይሄ ነው ሌላ አይደለም፡፡ በዚህች ኢፍትሐዊነት በገነነባት ዓለም ከታሪክ ዳቦ ትልቁን ድርሻ የሚወስዱት አሸናፊዎች እንደሆኑ መገንዘብ አለመቻል እጅግ አለመብሰል ነው፡፡ ባንወደውም እውነታው ይሄው ነው፡፡ እኩል መከፈል አለበት በማለታችንም ልናመጣው የምንችለው ለውጥ አይኖርም፡፡ ምክንያቱም ዘመኑን ወደ ኋላ መልሰን በዚያች ሀገር ያሉ ብሔረሰቦችን በአንድ የጊዜ ስፍር ላይ አስጀምረን አንተ ይሄን አንተኛው ደግሞ ይሄን ሥሩና መጨረሻ ላይ በሀገሪቱ ታሪክ ላይ እኩል ድርሻ ይኖራቹሀል ብለን ማበጃጀት ከቶውንም አንችልምና፡፡ ያለው አማራጭ ተወደደም ተጠላ ያለውን የተገኘውን ይዞ መጓዝ ብቻና ብቻ ነው፡፡

ታሪክ ማለት የሚያስደስተው የሀገርና የሕዝብ ገጽታ ማለት ብቻ ሳይን የማያስደስተውና የሚያስከፋውም አጠቃላይ የሀገርና የሕዝብ ያለፈ የነበረ ሁለንተናዊ መስተጋብር ወይም ገጽታ ማለት ነው፡፡ ይህ ታሪክ እነ እከሌን ስለሚያስከፋ ወይም ስለሚያስቀና ከሀገር ታሪክ ተቆርጦ ይጣል ይወገድ ማለት ድንቁርና ወይም የታሪክን ምንነት አለማወቅ ነው፡፡ ታሪክ አስከፋም አስደሰተ ተጠብቆ መያዝ ይኖርበታል፡፡ ቀጣዩ ትውልድም ከደካማውና ከጠንካራው ጎኑ ይማርበታል፡፡

ይሄንን እውነታ መገንዘብ መዋጥ የሚከብዳቸው ወገኖች ካሉ ለዚህ ድንቁርና የዳረጋቸው እራሳቸው በራሳቸው ላይ የጫኑት ጠባብና ዘረኛ አስተሳሰባቸው ነውና ይሆነናል ይበጀናል ብለው እስከያዙት ጊዜ ድረስ ከዚህ ደዌያቸው እንዲፈወሱ ልንረዳቸው የምንችለው ነገር ባለመኖሩ እጅግ እናዝናለን፡፡

ከላይ እንደገለጽኩት እነሱ እራሳቸው የዚህች ሀገር ታሪክ የአማራ ታሪክ ነው አሉ እንጅ በየትኛውም የታሪክ ሰነድ ላይ አማራ የኔ ነው ያለበት ዘመን ኖሮ አያውቅም፡፡ ነገሥታቱ ከአማራ የወጡ ቢሆኑም በአማራ ስም ግን ይህችን ሀገር ለአንድም ቀን ገዝተው አሥተዳድረው አያውቁም፡፡ ሀገሪቱ ለማስተናገድ ትቸገር ወይም አትፈቅድ የነበረው አረማዊ ኢአማኒ በሌላ አጠራር ጋላ (ልብ በሉ ጋላ የብሔረሰብ መጠሪያ አይደለም አረማዊ ወይም አሕዛብ ማለትም ያላመነ ያልተጠመቀ ከሚለው ቃል ጋር በተለዋዋጭነት የሚያገለግል ቃል ነው የቤተክርስቲያን መጻሕፍት ግብጽ ውስጥ አሕዛብ ያፈረሷቸውን አብያተክርስቲያናት “ጋላት” ወይም “ጋሎች አፈረሱት” በማለት ይገልጻሉና) እናም እንዲህ ዓይነት ሰው እንዳይነግሥ ብቻ ነው እንጅ አማኝ እስከሆነ ጊዜ ድረስ የዘሩ ማንነት ቦታ የሚሰጠው አልነበረም በዚህም ምክንያት ነው በጥንታዊት ኢትዮጵያ ከአገው ከትግሬም ከኦሮሞም የተወለዱ ነገሥታት ሊኖሩን የቻሉት፡፡ ንጉሥነት በዘር የሚወረስ መሆኑና የሥልጣን ሽሚያ የነበረ መሆኑ እንዳለ ሆኖ፡፡ የአማራ የምንትስ የምንትስ የሚል ነገር የመጣብን ደናቁርቱ የጥፋት ኃይሎች ከመጡ በኋላና በእኩይ መነጽራቸው ወደኋላ እየተመለከቱ እኩዩ መነጽራቸው የሚያሳያቸውን እኩይ ነገር መናገር ከጀመሩ ጊዜ በኋላ ነው፡፡

እንዲህ ባለ ስብጥር የተሠራውን የሀገር ታሪክ ዛሬ እኩያኑ በጥቅሉ “የአማራ” ብለው በመፈረጅ “አማራ የራሱን ታሪክ፣ ባሕል፣ አስተሳሰብ፣ ማንነት፣ ሥልጣኔ ወዘተረፈ. በተቀረው ሕዝብ ላይ ሲጭን ቆይቷል እንዲጭን አንፈቅድም! የተጫነውንም እናስወግዳለን” ብለው አረፉት፡፡

ሲጀመር “የኢትዮጵያ” ተብሎ የሚጠራው ባሕል፣ አስተሳሰብ፣ ማንነት፣ እሴት ሥልጣኔ የአማራ ሕዝብ ብቻ አይደለም፡፡ የኢትዮጵያ ተብሎ የሚታወቀው የጥፋት ኃይሎች የአማራ የሚሉት ባሕል፣ አስተሳሰብ፣ ማንነት፣ ሥልጣኔ በራሱ ሒደት ከሌሎቹም ብሔረሰቦች መልካም መልካሙን የተሻለ የተሻለውን የላቀ የላቀውን ተሞክሯቸውን አውጣጥቶ ወስዶ እራሱን የቀረጸ የገነባ እንጅ የአማራን ብቻ እያለ እየለየ እራሱን የቀረጸ አይደለም፡፡ አንደኛው ብሔረሰብ የበለጠ አዋጥቶ ሊሆን ይችላል፡፡ ይሁንና መስፈርቱ “የማን?” ሳይሆን “የትኛው የተሻለ የሠለጠነ?” የሚለው ነውና የማንትስ የማንትስ ብለን ጥያቄ ልናነሣ የምንችልበት አግባብ ሊኖር አይገባም፡፡ ነው ወይስ ደናቁርቱ ሊሉን የፈለጉት በዚህ የኢትዮጵያ ተብሎ በሚጠራው የአማራ መካተት አልነበረበትም? ለምን?

ደናቁርት ሆይ! ደዳብት ሆይ! ምንም ነገርን ከማንም ሳይወስድ የራሱን ብቻ ባሕል በሉት አስተሳሰብ ቋንቋ በሉት ሥልጣኔ ይዞ እንደ ደሴት እራሱን ነጥሎ ብቻውን የኖረና የሚኖር የገነባና የሚገነባ ብሔረሰብ ከኢትዮጵያ ብቻም ሳይሆን ከመላው ዓለም አንድ ብሔረሰብ ወይም ጎሳ አንድ ብቻ እንኳን ልትጠቅሱልኝ ትችላላችሁ?

በታሪክ አጋጣሚ ከሞላ ጎደል ያለውን የሀገራችንን ዘመን ከአማራ የወጡ ነገሥታት የመሪነትን ሚና እንደመጫወታቸው ሌሎቹ ወገኖች ኋላ ቀር አስተሳሰቦችን እንዲተውና የተሻውን፣ የበለጠውን፣ የላቀውን አስተሳሰብ እንዲጨብጡ ማድረጉ፣ መጣሩ፣ ማሠልጠኑ ኩነኔው፣ ኃጢአቱ፣ ጥፋቱ ምኑ ላይ ነው? ሥልጣኔ እንዴት ሆኖ የተስፋፋ ነው የሚመስላቹህ? ጠቃሚና የተሻሉ አስተሳሰቦችን፣ ተሞክሮዎችን ልምዶችን አንዱ ከሌላው በመውሰድ ያንንም ሥራ ላይ በማዋል አይደለም ወይ?

አየ መለስ ነፍስህን አይማረው የደንቆሮ መጨረሻ፡፡ እሱ ደንቁሮ ግብረአበሮቹንም አደንቁሮ ሀገርን ማጥ ውስጥ ከቷት ሔደ፡፡ እንኳን እዚህ ለዚህ ወገን ለወገን ቀርቶ ስንት ኢትዮጵያዊ እሴት ነው ከእኛ ወጥቶ ለሌላው ዓለም የተረፈው? ሌሎቹ ብልጦቹ ከእኛ ወስደው የተጠቀሙ ስንት እግዳሉ ይታወቅ አይደለም ወይ? ይህች ሀገር የአማራ እሴቶች ያላቹህትን ሁሉ አጥታ ምን ይቀራታል? ታዲያ እነኝህ እሴቶች ጠቃሚ መሆናቸው ከታወቀ ከተመሰከረ፤ እኮ በምን ምክንያት ነው የአማራ ስለሆኑ ብቻ ይጥፉ ይወገዱ የሚባለው? ይሄ ምን ማለት ነው? አማራ ከዚህ በኋላ ለሀገሩ ለወገኑ መሥራት ማዋጣት አይችልም አይኖርበትም ማለት ነው? ከዚህ በኋላ በምንም ዓይነት መንገድ ቢሆን ሥልጣን ኃላፊነት መያዝ አይችልም ማለት ነው? አዎ ይሄንን ማለታቹህ እንደሆነ በምትሠሩት ሥራ ሁሉ አረጋገጣቹህ፡፡

ግን በ 21ኛው መቶ ክ/ዘመን እንዲህ ዓይነት የድንጋይ ዘመን የአረማውያን የደዳብት የደናቁርት አስተሳሰብን ሥራ ላይ ለማዋል መሞከር የለየለት እብደትም ነው? ይቻላልስ ወይ? እስከ አሁን እንደቻላቹህ ነገም የምትችሉ ይመስላቹሀል ወይ? እኔ ሆኖ ከማየቴ በፊት ወያኔና ሌሎች የጥፋት ኃይሎችም የፈለጋቸውን ያህል ሲጠቡ ሲደነቁሩ ሲደድቡ ቢኖሩ የዚህን ያህል ይጠባሉ ይደነቁራሉ ይደድባሉ ብዬ ለማሰብ እጅግ ይቸግረኛል፡፡ እጅግ ያሳዝናል እውነታው ይሄው በመሆኑ፡፡

የሚጠቅም ሆኖ እስከተገኘ ጊዜ ድረስ እምየ ኢትዮጵያና ሕዝቧ አይደለም ከአማራ ባሕር ተሻግራም ከአቦርጁኖችም ቢሆን ትወስዳለች፡፡ እንደመስጠታችንም የወሰድነውም አለ፡፡ ለሀገርና ለሕዝብ የሚጠቅም የሠለጠነ የበሰለ አስተሳሰብ ማለት ይሄ ነው፡፡ የእከሌ ነው የእከሌ ነው እያሉ ማጥፋቱ አይደለም እሽ ደናቁርት?

አማራ ምን ባደረገ ነው የዚህን ያህል የሚጠላው? ሌሎቹን ብሔረሰቦች ይዞ መልካም ሥራ የሠራ፣ ለዚህች ሀገር ምኑንም ነገሩን ሳይሰስት የመጨረሻ መሥዋዕትነት እየከፈል ሀገሪቱን በነጻነቷ የኮራች የደመቀች ባለታሪክና የሥልጣኔ መሠረት እንድትሆን ማድረግ የቻለ ሊደነቅ ሊከበር ጎሽ ሊባል ሊመሰገን ይገባል እንጅ እኮ በምን ሒሳብ ነው ስንት የሆነላትን ሀገር ታሪክና እሴት ገደል ከቶ፣ በመቶ ዓመት ተገድቦ፣ ከንቱ አመድ አፋሽ ተደርጎ በገዛ ወገኖቹ እንደጠላት በክፉ ዐይን ሊታይ የሚገባው?

ዛሬ ላይ ወያኔ በሠራው የአማራን ስም የማጠልሸት ሠይጣናዊ የክፋት ሥራው አማራነትና እሴቱን እንኳን በሌላው ብሔረሰብ በገዛ አባላቱ እንኳን አላስፈላጊ የሚጠላና የሚያሳፍርም ማድረግ የቻሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡

አንድ ዓለማቀፋዊ እውነታ አለ፡፡ ከአንድ በላይ ብሔረሰቦች ባሉበት ሀገር የአንድ ብሔረሰብ የበላይነት (Domination) የማይቀር ተፈጥሯአዊና የታሪክ ሀቅ ነው፡፡ የትም ዓለም ያለው ተሞክሮ ከዚህ የተየ አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ ከዓለም የተለየች ልትሆን የምትችልበት ተአምር የለም፡፡ እንዲያውም ግፍንና በደልን በተመለከተ ተመሳሳይ የአሥተዳደር ሥርዓት ከነበራቸው ሀገራት እንጻር ሀገራችን ስትታይ እንደ መጽሐፍ ቅዱሱ ምስክርነት ከጥንት ጀምሮ ሕዝቧ እግዚአብሐርን አምላኪ ሕዝብ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በሌሎቹ ሀገራት ሲፈጸሙ የነበሩ የዘር ልዩነትን መሠረት ያደረጉ ግፎችና ኢሰብአዊ ድርጊቶች ፈጽሞ አልነበሩም አልተፈጸሙም፡፡ ለዚህም ነው ዛሬ ላይ በርካታ ብሔረሰቦች አናሳም ሆኑ ምን ሠፍረው ያሉበት ቦታ ለምና አረንጓዴ ሆኖ የምናገኘው፡፡ በዚህች ሀገር የብሔር ጭቆና ፈጽሞ አልነበረም፡፡

“የብሔር ጭቆና አለ! የኢትዮጵያ ተብሎ የሚጠራው ይሄ ይሄ ባሕል የማን ነው? የአማራና የትግሬ አይደለምን? የብሔር እኩልነት ይስፈን!” እያለ ጥያቄውን ያነሣውና ያራገበው ለወያኔና ለሌሎችም የጥፋት ኃይሎች መሠረት የሆነው የአማራ ተወላጁ ዋለልኝ መኮንን መሆኑ ይታወቃል፡፡ እኔ ይሄንን የዋለልኝ አስተሳሰብ የምኮንንበት ምክንያት ዋለልኝ ትግሬን ከጨመረ ለምን ሌሎቹህ እንደተወ ሊገባኝ ስላልቻለ ነው፡፡

ምክንያቱም በኢትዮጵያ ታሪክ ከትግሬ ይልቅ የአገው ብሔረሰብ ጉልህ አሻራ አለውና የማስተዋል ችሎታው ደካማ ከመሆኑ የተነሣ ካልሆነ በስተቀር የሌሎቹም አሻራ እንዲሁ በኢትዮጵያ ባሕል ሥልጣኔ ማንነት ነጻነት እሴት ላይ ጉልህ ነው፡፡ እንዲያውም ካለስ ትግርኛ የመንግሥት ቋንቋ ሆኖ አያውቅም ትግሬ በነበሩት ንጉሥ ዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ዘመንም እንኳ ንጉሡ ሲሠሩ የነበሩት በአማርኛ ነበር፡፡ መኳንንቶቻቸው ለምን? ብለው ለጠየቋቸው ጥያቄ ሲመልሱ “አማርኛ የአክሱም ነገሥታት ቋንቋ ነው ቤተመንግሥት ቤቱ ነው እኔ ላስወጣው አይገባኝም” ነበር ያሉት፡፡ ኦሮምኛን የወሰድን እንደሆነም ያውም በጎንደር ዘመን ለአጭር ጊዜም ቢሆን የመንግሥት ቋንቋ ለመሆን በቅቶ እንደነበር የታሪክ ምሁራን ይናገራሉና የተሻለ ተሳትፎ የነበራቸው እያሉ ትግሬ ብሎ ትግሬን ብቻ ጨምሮ ማቆሙ አግባብ አልነበረም፡፡ ከጨመረ ቢያንስ እነኝህን መጨመር ነበረበትና፡፡

በየተራ ግዙ ብሎ እያፈራረቀ የሚሾምና የሚሽር አካል በሌለበት ሁኔታም ሰማንያ ብሔረሰቦች አሉና ተብሎ ሰማንያውም በየተራ መንገሥ ነበረባቸው ብሎ ማሰቡ መቸስ ቂልነት ካልሆነ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡ በዚህች ስንት ነገር ባለፈባት ዓለም መሆናችንም ተረስቶ ተመሳሳይ የአሥተዳደር ሥርዓት ከነበራቸው ሀገራት እጅግ የተሻልን መሆናችን እየታወቀ ሀገራችን ያለችው ከገነት መሀል ይመስል እንዲያው ኮሽታም እንኳን መኖር አልነበረበትም ብሎ ማሰብ አሁንም እጅግ አለማስተዋልና መግቢያየ ላይ የገለጽኩላቹህን ሰው ከመሆናችን ጋር በተያያዘ ያለብንን ችግር አለማወቅ ነው፡፡

እነ ዋለልኝ ያላስተዋሉትና ድንቁርናቸው የነበረው ችግሩ የነበረባቸውን የምዕራባዊያን ሀገራትን ወቅታዊ ፖለቲካዊ (እምነተ አሥተዳደራዊ) እንቅስቃሴ ችግሩ ወዳልነበረባት ሀገር እንደ ፋሽን (ዘመንኛ) ነገር ቆጥረውት እንዳለ መቅዳታቸውና ያንንም ማራገባቸው ነው፡፡

ይህ እጅግ ብስለት የጎደለውና በተሳሳተ ግንዛቤ ላይ የተመሠረተ የዋለልኝ አስተሳሰብ የተማሪዎችን ዐመፅ ቀስቅሶ ዐፄውን ለውድቀት ዳርጎ ገና ከጅምሩ የሀገሪቱን ውድና አንጋፋ መሪዎች ቅርጥፍ አድርጎ የበላውን ደርግን ለሚያህል ጭራቅና በተመሳሳይ ሰዓትም የበፊቱን የበረሀ አውሬ የዛሬውን አንባገነን ጭራቅ የወያኔን አገዛዝ ሌሎችንም የጥፋት ኃይሎች ፈጥሮብናል፡፡

ዋለልኝና ተከታዮቹ ሐሳባቸው ያልበሰለና እንጭጭ መሆኑን ሳይረዱ ይሄው አሁን ድረስ ላለንበት ውጥንቅጥ እየተወሳሰበ ለሚሔድ ችግር ዳርገውናል፡፡ ከላይ እንደገጽኩላቹህ በእኔ እምነት በእኔ እምነት ብቻም ሳይሆን መሬት ላይ ያለው እውነታ እንደሚያሳየው የኢትዮጵያ ተብሎ የሚታወቀው ባሕል፣ ተጨባጭና ተጨባጭ ያልሆኑ ቅርሶች (tangible and intangible Heritages) ፣ እሴቶች ሁሉ የአማራ ብቻ አይደሉም፡፡ እነ ዋለልኝ ሊረዱት ያልቻሉት ይሄንን ሀቅ ነው፡፡

ማንነታችን በራሱ ጊዜ የተሻለ አስተሳሰብ ባሕል እሴት ካለው ብሔረሰብ እየወሰደ የሀገሪቱ አድርጓል፡፡ ሥርዓቶቹ የከፋውንና ኋላ ቀር የሆነውን የማይጠቅመውን ልማድ እያስቀሩ በተሻለው አስተሳሰብ ባሕል እሴት ለመተካት ጥረት አድርገዋል፡፡ ይሄ ደግሞ የአንድ መንግሥት ወይም አስተዳደር ኃላፊነትና ግዴታም ነው ለምሳሌ ያህል አንዱን ልጥቀስ ዕቁብ ወይም ቁቤ ዛሬ ላይ በሁሉም ኢትዮጵያዊያን ዘንድ የተለመደና ያለ ባሕላችን ነው፡፡ የሁላችንም ከመሆኑ በፊት ግን ዕቁብ የጉራጌ ባሕል ነበር፡፡ ልማዱ ባሕሉ አስተሳሰቡ የሠለጠነ የበሰለ ጠቃሚም ስለሆነ ከጉራጌ ተወስዶ የኢትዮጵያ ሆነ፡፡ በዚሁ መልኩ ጠቃሚና የላቁ ባሕላዊ አስተሳሰቦችና ልማዶች ከየብሔረሰቡ እየተለቀሙ ተውጣጥተው ነው የኢትዮጵያ ተብሎ የሚታወቀውን ባሕል አስተሳሰብና እሴቶችን ሊቀርጹ ሊገነቡ የቻሉት፡፡ አሁን ላይ ሲታዩ የአንድ ብሔረሰብ ሊመስሉ ይችላሉ ነገር ግን በፍጹም የአንድ ብሔረሰብ ባሕል ማንነት እሴት ብቻ አይደሉም፡፡ በዚህች ሀገር ያሉ ብሔረሰቦች ሁሉ በዚህች ሀገር እንደመኖራቸው ለዚህች ሀገር ለነጻነቷ መሥዋዕትነት ከመክፈል ጀምሮ ከማንነት እስከ ሥልጣኔዋ ድረስ አስተዋጽኦ ላያደርጉ የሚችሉበት ምንም ምክንያት አልነበረም፡፡

ከዚህ ውጭ ግን የሁሉም ብሔረሰቦች ሁሉም እሴቶች እኩል የእውቅና ዕድል መሰጠት ነበረበት ከሆነ ጥያቄያቸው ይሄ ጥያቄ የመብትና የፍትሕ ሳይሆን የአመክንዮ፣ የሥነሥርዓትና የፍላጎት ነው የሚሆነው፡፡ ለዚህ ደግሞ መልስ ሊሰጥ የሚችል አካል የለም፡፡ ነገሮች እራሳቸውን የሚያስተናግዱበትን ተለምዷዊና ተፈጥሯዊ አሠራር አላቸው፡፡ ይህ ጉዳይ የሚዳኘው በዚህ አሠራር ነው፡፡ ይሄንን ጥያቄ እንኳን እኛ ከሀብታሞቹ ሀገራት አንዳቸውም እንኳን አልመለሱም፡፡ በሁሉም ሀገሮች በተለያዩ ምክንያቶች ጎልተው የሚወጡ የተወሰኑ ብሔረሰቦች እሴቶች መሆናቸው ግድ ሆኖ ኖሯል፡፡

እስከማውቀው ድረስ ጎልተው የተዋወቁ እሴቶች ይኖሩ ይሆናል እንጅ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የሌሎች ብሔረሰብ እሴቶች የኢትዮጵያ አይደለም ተብሎ አያውቅም፡፡ የቀረው የአቅም ጉዳይ ነው የተሻለና ጠቃሚ የሆነው ግን አስቀድሜ እንዳልኩት አናውቀውም እንጅ በራሱ ጊዜና ባለው የተሻለ አቅም እየተመረጠ የሐገሪቱ ሆኗል፡፡ በተረፈ እንዲህ ብለው ማሰባቸው ራሱ በጣም አስገራሚ ነው፡፡ እንዲህ ብለን እንድናስብ የሚያደርገን አለመብሰላችን ነው እንጭጭነታችን ነው ጠልቀን አስፍተን ማሰብ አለመቻላችን ነው ድንቁርናችን ነው፡፡ ቋንቋ ባሕላችንን ብናይ የአንደኛው ከሌላኛው የተወራረሰ የተቀላቀለ የተዋዋሰ ነው፡፡ ይሄንን ተፈጥሯዊ ሁኔታ ነው ደናቁርቱ እየኮነኑ ያሉት፡፡

“ጭቆና አልነበረም! እያልከን ነው ወይ?” ካላቹህኝ አልወጣኝም! ነበረ፡፡ የነበረው ጭቆና ግን ፈጽሞ የብሔር ሳይሆን የመደብ ነበር፡፡ ይሄም ቢሆን ግን የጥፋት ኃይሎች ለርካሽ ጥቅማቸው ሲሉ ጭቆናው ነበር ተብሎ እጅግ ተለጥጦና ተጋንኖ ፈጠራም ታክሎበት የሚያወሩትን ያህል አይደለም አልነበረምም፡፡ ሥልጣኑ ይያዝ ይገኝ የነበረው አማራ በመሆን ከማንኛውም የአማራ ተወላጅ ተመርጦ ሳይሆን ከሰሎሞናዊው የዘር ኃረግ ጋር የተሳሰረው ቤተሰብ ተወላጅ በመሆን ብቻ የነበረ በመሆኑ፡፡ ጭቆናው የመደብ እንጅ የብሔር አልነበረም አይደለምም፡፡

በሀገራችን የነበረው ገዥና የሚወራውን ያህል ባይሆንም ግፍ ፈጸመ የሚባለው ማን እንደሆነ በሚገባ የሚታወቅ ሆኖ እያለ አማራን ሲጨቁን ሲረግጥ የኖረ አድርገው ያስባሉ፡፡ እውነታው ግን ይሄ አይደለም፡፡ ለአማራ ያለው የጥላቻ መንፈስ መሠረቱ ቅንነት ማጣት፣ ማየት ማሰብ ካለመቻል የሚመነጭ ድንቁርናና ጠባብነት ነው፡፡ በሀገራችን የመደብ እንጅ የብሔር ጭቆና እንዳልነበረ ለማንም ግልጽ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ በገዥዎች የተጨቆኑ የተረገጡ ብሔረሰቦች አሉ ከተባለ እጅግ በከፋ ሁኔታ የተጨቆነ የተረገጠ የተበዘበዘና የግፍ ገፈት ተጋቹ የነበረው የአማራ ሕዝብ እንደሆነ ማረጋገጥ እወዳለሁ፡፡

እንደምታውቁት በዘውዳዊው ሥርዓት የሀገሪቱ ጦር ወይም ተዋጊዎች ደሞዝ አልነበራቸውም፡፡ ጦሩን የመመገብ የማሥተዳደር ግዴታና ኃላፊነቱ የተጫነው በገበሬው ላይ ነበር፡፡ ገበሬው ለሀገር ጠባቂ ጦር ልጆቹን ከመስጠቱ በተጨማሪ የሀገሪቱን ሠራዊት ተከፋፍሎ የመቀለብ ግዴታ ነበረበት፡፡

ዘውዳዊው ሥርዓት ከአማራው እንደመውጣቱና ከአማራው ሕዝብ መሀል እንደመኖሩ የአማራ ሕዝብ ከሌሎቹ ብሔረሰቦች በተለየ መልኩ ይሄንን ግዴታ የመሸከም ኃላፊነት ነበረበት፡፡ በመሆኑም እነኝህ የሠራዊቱ አባላት ሦስትም ሆነ አምስት በመሆን በአንድ ገበሬ ጎጆ ይመሩ ነበር፡፡ ይህ አሠራር “ተሠሪ” ይባላል በጎጃም “እሬና” ይባላል፡፡ እነኝህ ሀገር ጠባቂ ፋኖዎች በተሠሩበት ገበሬ ቤት ይበላሉ ይጠጣሉ አባወራና ልጆች የሚያገኙት ከነሱ የተረፈውን ነው፡፡ በአንዳንዶቹ ቤት የተሠሩትም ሲያሰኛቸው ያለ ባለቤቶቹ ፈቃድ ጠቦቱን አርደው ይበላሉ ገበሬው ምንም ማለት አይችልም፡፡

ተሠሪዎቹ እንዲህ እንዲህ እያሉ ያች ጎጆ ስትደኸይባቸው ስታጣ ስትነጣባቸው ደሞ ወደ ሌላዋ ይሄዳሉ ደሞ ያችንም በተራዋ ያደኸያሉ፡፡ ዝርዝሩን ቢናገሩት ትንሽ አስቸጋሪ ነው እንዲሁ ልለፈው ባጠቃላይ ግን ለዚህች ሀገር ህልውናና ነጻነት መጠበቅ የአንበሳውን ድርሻ የሚወስደው ገበሬው ነው፡፡ አማራ ይሄንን ከባድ መራር ዋጋ ለገዥዎቹ ሳይሆን ለሀገሩ ነጻነትና ህልውና ሲል የሚከፍለው ዋጋ እንደሆነ ተቀብሎ፣ የውዴታ ግጌታው አድርጎ ለሽዎች ዓመታት ሲከፍል የኖረ ሕዝብ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ነው የአማራ ገበሬ ጥሪት መቋጠር ለልጁ ማውረስ የሚችለው ነገር የሌለውና ኑሮው ከእጅ ለወደ አፍ እንኳን የሚበቃ ያጣ ሊሆን የቻለውና ዛሬም ድረስ ሥር በሰደደ ድህነት ታስሮ የቀረው፡፡

ዛሬ በወያኔ ደናቁርት አንደበት “ለእግሩ ጫማ የማያውቅ” ተብሎ እስከመዘለፍ ላበቃው ድህነት የተዳረገው ለሀገሩ ሲል ሁለንተናውን ሲከፍል በመኖሩ ነው፡፡ ካላቹህ የአማራ ገበሬ ጫማ ብቻ አይደለም እንደምንም አንዲት ጨርቅ ከገዛ እሷኑ እየደራረተ ከገላው ላይ ተበጣጥቃ እስክታልቅ ድረስ ሌላ መቀየሪያ አያውቅም፡፡ የኢትዮጵያ ገጠሮችን እየተዘዋወራቹህ ስትጎበኙ አንድ የምትታዘቡት ነገር አለ የደቡቦችና የኦሮሞዎች የገበሬዎች ቤቶች አቋም ጠንከር ደርጀት ያሉ ናቸው ወደ አማራው ዞር ስትሉ ደግሞ የገበሬው ጎጆ ደሳሳ ሆኖ ታገኙታላቹህ፡፡ በሌሎች ነገሮች ላይ ያለው የይዘትና የጥራት ልዩነትም እንደዚሁ ነው፡፡  አማራ የገዥዎች ጭሰኛ ሆኖ ነው የኖረው ኑሮውን ቀረብ ብለው ላዩት አንጀት ይበላል፡፡

በታሪክ አጋጣሚዎች ያጣቸውን ነገር ግን የራሱ መሬቶች መሆናቸውን እያወቀም እንኳን ሁኔታው ወደ ነበረበት ቦታው ሲመለስ አስለቅቄ መሬቴን መልሸ ልያዝ ሳይል ለም መሬቶቹን አስረክቦ እሱ ለእርሻም ለምንም በማይመች መሬት ላይ የሚኖር ደግና ቅን ሕዝብ ነው፡፡

ይሄንን መሥዋዕትነት ለማንና ለምን ሲከፍል እንደኖረ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ብቻ ነው ምንም እንዳልሆነ በችጋር እየተጠበሰ ምንም እንዳልጎደለበት ሆኖ የኖረው፡፡ ከዚህች ሀገር የሚበልጥበት ምንም ነገር የለምና ሁለንተናውን ለእናት ሀገሩ ከፍሎታል አውሎታል ሠውቶታል፡፡

የሚያሳዝነው በጠላት ሸፍጥና ሴራ እጁ አመድ አፋሽ መሆኑ ውለታው ሁሉ ገደል ገብቶ ያለስሙ ስም ተሰጥቶት መጠላቱ ነው፡፡ ጭንቅላት ቢኖረን ወደ ኋላም ወደ ፊትም ደወ ግራም ወደ ቀኝም መመልከት ብንችል አርቀን አስፍተን ጠልቀን ማሰብ ብንችል፣ ኢትዮጵያዊነቱ ቢሰማን የሀገራችንንና የሕዝቧንም ህልውና የምንፈልግ የምንመኝ የምንወድ ብንሆን በምንም ተአምር ለአማራ ጥላቻ ሊያድርብን አይችልም፡፡ ለዚህች ሀገርና ሕዝብ ህልውናና ነጻነት አማራ ለከፈለው ገደብ የለሽ መራራ ዋጋ እናመስግነው ብንል ለምስጋናችን ተስተካካይ ቃል ፈጽሞ ልናገኝለት አለመቻላችንን በሚገባ በተረዳን ነበር፡፡ አማራን ልንጸየፍ ልንጠላ አይደለም ወደነውም ለፍቅራችን የልባችን ባልደረሰ፡፡ ውግዘትና ጥላቻውን ትተን ክብር በሰጠነው በኮራንበትም ነበር፡፡ ለዚህ ነው ለአማራ ያለው የጥላቻ መንፈስ መሠረቱ ድንቁርና ጠባብነት የሀገር ጠላትነትም ነው ያልኩት፡፡

እኔ ግን የምፈራው የሌለ ያልነበረ ነገር እያወራን አማራን ያለስሙ ስም እየሰጠን እያከፋፋን ፊት እየነሳን እያሸማቀቅን የሌለ አውሬ ፈጥረን እያወራን በገዛ እጃችን አውሬውን ፈጥረነው ቁጭ እንዳንል ነው፡፡ አማራን በየሔደበት በክፉ ዓይንና አቀባበል እየተቀበልን በጎሪጥና በጥላቻ ዐይን ዕያየን ሳይወድ በግድ ጥላቻ እንዲያድርበት እያደረግን ከዚህም በኋላ መልካም ምላሽ የምንጠብቅ ካለን እጅግ ተሳስተናልና እንታረም ማለትን እወዳለሁ፡፡ እንደዛ ተሰባብሬ ደቅቄ መራር መሥዋዕትነት ከፍየ ባቆየኋት ሀገር ባልዋልኩበት ከዋልኩ፣ ባልሠራሁት ከታማሁ፣ ስም ከወጣልኝ አይቀር ብሎ የተነሣ እንደሆነ ኋላ ማጣፊያው ይቸግራልና መታረሙ ሳይሻል አይቀርም፡፡

አንድ የውጭ ጋዜጠኛ ነው አሉ የጃንሆይን ልጅ ልዕልት ተናኘወርቅን “የኢትዮጵያ ሕዝብ ስንት ይሆናል” ብሎ ቢጠይቃት “ከአምስት መቶ አንበልጥም” ብላ ቁጭ አለች፡፡ እንግዲህ ልብ በሉ ልዕልቲቱ በዘር አማራ እንደሆነች ብታስብም ለእሷ የኢትዮጵያ ሕዝብ ማለት የንጉሣዊያን ቤተሰብ ብቻ እንጅ አማራውም እንኳን አይደለም፡፡ የነበረው አስተሳሰብ ሐቅና እውነታ ይሄ ነው፡፡ የንጉሣዊያን ቤተሰብ ያልሆነው የአማራ ሕዝብ በገዥዎቹ ይናቅ ይገፋ ይዋረድ ይጣጣል ነበር እንጅ አማራ በመሆኑ አልተከበረም፡፡ ወያኔና የጥፋት ኃይሎች እንደሆኑ ጥላቻን ለመፍጠር የሕዝብ አንድነትና ዝምድና እንዲፈርስ ለማድረግ ነው ሆን ብለው እውነትን እያዛቡ የማይመስል ፈጠራ እያመጡ ገዥዎችንና አማራን አንድ አድርገው በማየት የኢትዮጵያን ሕዝብ የተሳሳተ ድምዳሜ እንዲያዝ ለማድረግ እየደከሙ ያሉት፡፡

ይህ እንዳለ ሆኖ አስቀድሜ እንዳልኳቹህ የጥፋት ኃይሎች የገዥዎቻችንን ግፍና በደል አጋነውና ፈጠራ ጨምረው እንደሚያወሩት ያህልም እንኳን ቢሆን በሀገራችን የነበረው አገዛዝ ከጥንት ጀምሮ ሀገሪቱ ሃይማኖተኛ በመሆኗ ምክንያት ተመሳሳይ ዘውዳዊ የመንግሥት ሥርዓት ከነበራቸው ሀገራት እጅግ የተሻለው ነበር፡፡

አውሮፓና ሌሎች ሀገራት ላይ እንደነበረው የሰው ልጆችን ለመዝናኛነት ከአውሬ ጋር እያታገሉና እያስበሉ መዝናናት ነገሥታቶቻቸው ሲሞቱ ጠባቂ እንዲኗቸው ተብሎ የሰው ልጆችን ከነ ሕይወታቸው አብሮ መቅበር የመሳሰለው ግፍ በሀገራችን አልተፈጸመም፡፡ የሩቁን ብንተወው በናዚ ዘመን በሰው ልጆች የተፈጸመውን ግፍ ማሰብ ይቻላል፡፡ ወደ ሀገራችን ስንመጣ ግን የዚህ ወይም የዚያ ዘር በመሆኑ ብቻ ዘግናኝ ግፍ የደረሰበት ዘር ኢትዮጵያ ውስጥ የለም፡፡

የጥፋት ኃይሎች ፋሽስት ጣሊያን “አማሮች ለአገዛዜ እንቅፋቶች ናቸው!” ብሎ በማሰቡ አማራን ጠላት አድርጎ በማቅረብ በሌሎቹ ብሔረሰቦች ለማስጠቃት በማሰብ በእውነተኛ ታሪካዊ ኩነት ላይ ተመሥርቶ ፈጠራ ጨምሮበት በማውራት በወቅቱ በአማራ ላይ ሰፊ ጥቃት እንዲፈጸም ያደረገበትን የሔጦሳንና የጨለንቆን ፈጠራ ዛሬም ወያኔ እና ኦነግ የጥፋት ኃይሎች በሽግግሩ ወቅት አሁንም እየደጸሙት ያለውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ለመሸፋፈንና ምክንያታዊ ለማስመሰል ጣሊያን ለጥፋት ዓላማው ፈጥሮ ያወራውንና ምንም ዓይነት መረጃ የሌለውን፤ የጦሩ አዝማች ኦሮሞ (ራስ ጎበና ዳጬ) በሆኑበት ሁኔታና እንደ አቶ አሰፋ ጫቦ ጥናትና ምርምር ከዚያ ሠራዊት ከ95 በመቶው በላይ ኦሮሞ በሆነበት ሁኔታ ጣሊያን ፈጥሮ ያወራው ሐሰተኛ ወሬ ይሆናል ይፈጸማል ብሎ ለማሰብም ፈጽሞ በማይቻልበት ሁኔታ ሐሰት መሆኑን እያወቁ የጣሊያንን የጥፋት ፈጣራ ወሬ አንሥተው ለተመሳሳይ የጥፋት ዓላማ ተጠቅመዋል፡፡ ወሬው ግን እንዳልኳቹህ ነጭ ውሸት ነው፡፡

ጦርነቱ ነበረ ወይ ከተባለ አዎ ነበረ፡፡ በዘመነ መሳፍንትና በዋዜማው ማዕከላዊ መንግሥት ተዳክሞ ሀገሪቱ ተፈረካክሳ እነኝህ ዐፄ ምኒሊክ ጦር ያዘመቱባቸው የሀገራችን አካባቢዎች ተረስተው ርቀው ስለነበረና ዐፄ ቴዎድሮስ የጀመሩትን ሀገርን እንደገና የማዋሐድ አንድ የማድረግ ተልእኮ ዐፄ ምኒልክም የማስፈጸም ግዴታ ስለነበረባቸው ያንን አድርገዋል፡፡ የተባለው ግፍ ግን የፋሽስት ፈጣራ ነው፡፡ እንዳልኩት ከጦሩ አባላት ማንነት አንጻር ይሄንን ለመፈጸም የሚያበቃ ክፍተትና አጋጣሚ ፈጽሞ አልነበረምና፡፡

እንኳንና እንዲህ ዓይነት ግፍ ሊፈጸም ዐፄ ምኒሊክ የዚያ አካባቢ ሰው እንቢ ብሎ ጠንክሮ በመዋጋቱ ምክንያት ብዙ ዓማፅያን ማለቃቸው አሳዝኗቸው መኳንንቱ በጦርነቱ ወላጆቻቸው የሞቱባቸውን ልጆች አምጥቶ እንደልጁ አድርጎ እንዲያሳድግ ማዘዛቸውና ይሄም መፈጸሙ ይታወቃል፡፡ ባልቻ አባነብሶና ፊታውራሪ ኃ/ጊዮርጊስ ዲነግዴ ያኔ ወላጆቻቸው በጦርነቱ ከሞቱባቸውና መኳንንቱ አምጥተው እንደልጅ አድርገው ካሳደጓቸው ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

እንዲህ ዓይነት ኃላፊነት የተሞላበት ሥራ ነው የተሠራው፡፡ በዚህ ሀገርን መልሶ አንድ በማድረጉ ትንቅንቅ ግፍ ተፈጸመ ከተባለ ግፍ የተፈጸመው በመጀመሪያውና የተልእኮው ከባዱ ወቅት በነበረው ዐፄ ቴዎድሮስና መሳፍንቱ ባደረጉት ትንቅንቅ መሳፍንቱ ሕዝቡን እያስገደዱ ድጋፍ እንዲሰጣቸው ያደርጉ ስለነበር ሕዝቡን ለጥቃት በማጋለጣቸው ሕዝቡ እየተሰበሰበና በቤት ውስት ታጭቆ እየተዘጋበት እንዲቃጠል የተደረገው ነው፡፡ ይህ ደግሞ የተፈጸመው በኦሮሞው ወይም በትግሬው ላይ ሳይሆን በአማራው ያውም በጎንደሬው ላይ ነው፡፡

የጥፋት ኃይሎች ይሄንን ሁሉ አጥተውት አይደለም እንደ የጥፋት ኃይልነታቸው ፋሽስታዊ የጥፋት ሥራ መሥራት ስላለባቸው ከጌታቸው ከፋሽስት ጣሊያንን ፈጠራ ተቀብለው ሐውልት በመሥራት ሕዝብ ለማፋጀትና ያ አካባቢ የኢትዮጵያ እንዳልነበረና ዐፄ ምኒልክ የቀላቀሉት አስመስሎ ለመገንጠል ነው ፈጠራውን የሚያወሩት፡፡ ደናቁርቱ የኢትዮጵያ ታሪክ ፈጠራ ነው አንቀበልም ካሉ ማየት የሚችል ዓይን መዳሰስ የሚችል እጅ ካላቸው ከከፋ እስከ ሐረር በመላው አካባቢው ከክርስቶስ ልደት በፊት ስድስት መቶ ዓመታት ካስቆጠሩት እስከ ሰባት መቶ ዓመታት ዕድሜ እስካላቸው በዓይን የሚታዩ በእጅ የሚዳሰሱ ገዳማትና ቅርሳቅርሶችን በማየት የሚሉት አካባቢ የኢትዮጵያ አካል መሆኑን ማረጋገጥ ይችላሉ፡፡ ዳሩ እውነቱ ጠፍቷቸው አይደለም ታሪክን የሚክዱት የጥፋት ዓላማቸውን ለማስፈጸም ታሪክ እውነትን እየመሰከረ አላሠራ ስላላቸው እንጅ፡፡

ዐፄ ምኒልክ (ለነገሩ ያኔ ገና ዐፄ አልሆኑም) በዚህ ተልእኮ ጦራቸውን ወደተባሉት ሥፍራዎች አዝምተው የራቀውን የተረሳውን ባይመልሱ ኖሮ የእነዚህ የሀገራችን ክፍሎች ነዋሪዎች በባለአባቶቻቸውና በጎሳ መሪዎቻቸው ለባርበት ተሸጠው ሊያልቁ ከባድ አደጋ ላይ ነበሩ፡፡ ይህ አደጋ የተገታው ዐፄ ምኒልክ ዐፄ ቴዎድሮስ ያደርጉት እንደነበረው ሁሉ በጸረ የባሪያ ንግድ ላይ የጸና አቋም የያዙ ስለነበሩና እንዲቆም በማድረጋቸው ነው፡፡ እናም እውነቱና የጥፋት ኃይሎቹ የሚያወሩት እጅግ የተራራቀና የማይገናኝ ነው፡፡ እግዚአብሔር ይመስገንና ሀገራችን ከእንደዚህ ዓይነቱ የዘር ልዩነትን መሠረት ካደረገ ጥፋት የተጠበቀች ነው የነበረችው፡፡ በተለያዩ የጥንት ፈላስፎች መጻሕፍትና የሃይማኖት መጻሕፍት ተጽፎ ያለውም ሀገራችን የፍትሕ ሀገር መሆኗን ነው፡፡

ዛሬ ላይ ግን የሚገርመው እነዚያ ከእኛ እጅግ የከፋ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የነበረባቸው የአሥተዳደር ሥርዓት የነበራቸው የአውሮፓ ሀገራት ኮሽታ እንኳን የነበረባቸው ሳይመስሉ ተግባብተውና ተስማምተው በመሥራት ለማደግ ለመበልጸግ ሲችሉ ያሳለፉት ዘግናኝና የእርስ በእርስ እልቂት ተስማምተው ተባብረው ከመሥራት ቅንጣት ታክል እንቅፋት እንዲፈጥርባቸው ሳይፈቅዱለት ሲጓዙ እኛ ግን ጭራሽም ያልነበረ የሌለ እየፈጠርን በመናቆር ቁልቁል መሔዳችን ነው፡፡

እንደ ወያኔ ዓይነት ያለ የሌለ እያወራ ሕዝብን ከሕዝብ ጋር በማፋጀት ሴራ ላይ የተጠመደ ደንቆሮ ደደብ የማይገባው የማይረዳ አህያ አመራር ሳይሆን ልባም አርቆ አሳቢ በመግባባት በመስማማት በአንድነት በፍቅር መሠረትነት ሕዝብን የሚመራ ኃላፊነት የሚሰማው አመራር ስላላቸውና በዚህ ላይ ተግተው ስለሠሩ ነው፡፡ እኛ ግን እውነቱንም ውሸቱንም እየተጋትን ያን ፈጸሙ የሚባሉት ሰዎች ዛሬ ያሉና እነሱን መፋረድ ይቻል ይመስል እዚህ ግባ የማይባል በደልን እየጠቀስን ያም ቢሆን ገፈቱን የተጋተው አማራ ሆኖ እያለ ልክ በእኛ ብቻ የተፈጸመ እያስመሰልን የጥንት ነገርን እየጎተትን መናቆር መፋጀትን ሥራየ ብለን ይዘነው በየት በኩል አልፈን መቸስ ሠርተን ይለፍልን?

በዚህ አጋጣሚ ጥፋትን መተላለቅን መለያየትን ለምትሰብኩ የጥፋት ልጆች የምለው መልእክት ቢኖረኝ እስኪ ልብ በሉና ቆም በሉና እየሠራቹህት ያላቹህትን ነገር አስቡት፡፡ እርግጠኛ ነኝ ከዚህ እንደማናተርፍ ታውቃላቹህ ወይም ማወቅ ይኖርባቹሀል፡፡ የምታውቁ ከሆነም ታዲያ ምን ነው? ምን ነው? ምን አለ ይሄንን ምስኪን ሕዝብ ያሳለፈው መከራ ችጋር ቢበቃውና ፍቅርን አንድነትን ሰላምን ሰብካቹህለት ተባብሮ ሠርቶ አንገቱን ቀና ቢያደርግ? ችጋሩን ቢያራግፍ ምን አለበት? ይሄንን ብታደርጉ ምን ትሆናላቹህ? ተጠቃሚ ትሆናላቹህ እንጅ ምናቹህ ይጎዳል? እንግዲህ ምሁርነት ማለት ሕዝብን መውደድ ማለት አርቆ አሳቢነት ማለት ዐዋቂነት ማለት ይሄ ነው ሌላ ምን አለ ብላቹህ ታስባላቹህ?

የጥፋት ኃይሎችን ልጠይቅ የምሻው ጉዳዮች ቢኖሩ፡- መሮጥ የቻለ የቻለውን ያህል መሮጥ እንዲችል የውድድር መድረኩ ለሁሉም ክፍት መሆንና ሁሉም ችሎታውና አቅሙ የፈቀደለትን ያህል መሮጥ እንዲችል መደረግ ሲኖርበት “እኩል ዕድልና መድረክ ለሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች” የሚለውን ፍትሐዊ የሚመስል ግን ያልሆነን ፅንሰ ሐሳብን እጅግ በተሳሳተና በደነቆረ አረዳድ በመተርጎም ያለቦታው “አንተ ቀድመህ ከሮጥክ እኛን ጥለኸን ስለምትሔድ፣ በልጠህ ልቀህ ስለምትታይ ቀድመኸን መሮጥ ብትችልም አንፈቅድም ከእኛ ጋራ ነው መሮጥ ያለብህ፤ እኛ ካንተ ጋር እኩል መሮጥ አንችልምና አብረኸን አዝግም! ወይም እስከምንደርስብህ ድረስ ተኛ ካልሆነ ደግሞ ጥፋ!” የሚል አስተሳሰብስ ከ21ኛው መቶ ክ/ዘ ሰዎች ያውም ተምረዋል ከሚባሉት የሚጠበቅ ነው ወይ? አሠራሩስ ድንቁርና የተሞላበት ኢፍትሐዊ አሠራር አይደለም ወይ? ይሄስ ዓይነት አሠራር በየት ሀገር ነው ሥራ ላይ ውሎ ተግባራዊ ሆኖ የሚያውቀው ፍትሐዊስ የሚሆነው?

ሌላው ብሔረሰብ የሚጠና የሥነ ጽሑፍ ሀብት ወይም ሰፊ ታሪክ ከሌለው የበለጸገ የሥነ ጽሑፍ ሀብትና ሰፊ ታሪክ ያለው (የአማራ) መጠናት የለበትም ወይ? ይሄ ጠልፎ መጣል ማሰናከል አይደለም ወይ? “የኔ ዓይን ጠፍቷል ያንተም ይጥፋ!” ማለት አይደለም ወይ? ይሄ ጎትቶ መጣል አይደለም ወይ? ከዚህስ የከፋ ደንቆሮነት አለ ወይ? የሄ እንዴት ሆኖ ነው ፍትሐዊ አሠራር የሚሆነው?

እንዲህ ዓይነት “ተበለጥን ተቀደምን” በማለት ዓይናቸው ደም የሚለብስባቸው የሚቀላባቸው ሰዎች ካሉ ችግሩ በዚህ ሰይጣናዊ ቅናት የተለከፉቱ የእነሱ እንጅ ጠንክረው በመሥራታቸው መቅደም መሠልጠን የቻሉት ወገኖች አይደለምና ወደ ውጪ መመልከታቸውን ትተው ወደ ውስጣቸው ይመልከቱና ለዚህ የኅሊና ደዌያቸው መድኃኒት ይፈልጉ “ያለመበለጥ ያለመቀደም” መፍትሔው ጠልፎ በመጣል የቀደመውን ማስቀረት ማሰናከል ሳይሆን በርትቶ በመሥራት ከተቻለ ለመቅደም ወይም እኩል ለመሮጥ ካልተቻለ ደግሞ አቅምን አውቆ መበለጥን መቀደምን አምኖ በጸጋ መቀበል እንደሆነ መረዳት ነው፡፡

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

amsalugkidan@gmail.com

 

The post አማራ አለ ወይስ የለም? appeared first on Zehabesha Amharic.

በኦርጋን ቢዜም ምን ችግር አለው? (ቃልኪዳን ኃይሉ)

$
0
0

ዜማ ማለት ስልት ያለው ጩኽት፤ የንዋየ ማሕሌት ድምፅ እና የሠዎች ዜማ /ዜማ ግእዝ፤ ዕዝልና አራራይ ማለት ሲሆን፤ የዜማ ዕቃዎች ማለት በስልት የሚዜምባቸው ዕቃዎች በገና፣ ከበሮ፣ መሰንቆ፣ ጽናጽልና አርጋኖን (በነገራችን ላይ ኦርጋንና አርጋኖን የተለያዩ ነገሮች ናቸው)፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን የራሷ የሆነ የዜማ እቃዎች አሏት፡፡

Abune Melekestedik Organ

የቤተክርስቲያኗን የዜማ እቃዎችም ሆነ አዚያዚያሟን ማንም ተውሶ ሊጠቀምበት የሚችል ነገር ግን ቤተክርስቲያኗ በድጋሚ አዲስ መሳሪያ በአለም ላይ ቢሰራና ቢፈጠር የማትጠቀም ነች፡፡ ቤተክርስቲያኗ በገና፣ ከበሮ፣ መሰንቆ፣ ጸናጽል፣ እምቢልታና ዋሽንት ብቻና ብቻ ነው የምጠቀመው ስትል መፃሕፍ ቅዱስን ትጠቅሳለች (ዘፍ 31፤27፣ 2ዜና 29፤25፣ ዘፍ 4፤21፣ መዝ 150፤4፣ ዳን 3፤5 ኢሳ 5፤12፣ ማቴ 9፤23፣ ራእ 5፤8፣ መዝ 32፤2….) ሌሎች ብዙ ጥቅሶች ከመጽሐፍ ቅዱስ ማጉረፍ ይቻላል፡፡ በዚህም የመጻሕፍ ቅዱስ መመሪያ መሰረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትን የዜማ መሳሪያዎች ትጠቀማለች፡፡ መጠቀምም ብቻ ሳይሆን ትርጉምና ምስል ትሰጣቸዋለች፡፡ ለምሳሌ ከበሮ በኢየሱስ ክርስቶስ ይመሰላል፡፡

እንጨቱ ከቆዳ ጋር የተለጎመበት ጠፍር ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ጊዜ በጅራፍ ሲገርፉት በገላው ላይ ይታይ የነበረው ሰንበርን ይመስላል፡፡ ከበሮውን የተሸከመው ገመድ ኢየሱስ የተገረፈበትን ገመድ ይመሰላል፡፡ ከበሮ አመታቱም ሚስጥር አለው፡፡ መጀመሪያ ከበሮ በመሬት ተቀምጦ ነው የሚመታው፡፡ ሲመታም ቀስ ቀስ እየተባለ ሲሆን ትርጉሙም ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ በመሬት እየጎተቱ መምታታቸው ነው፡፡ ቀስ ቀስ እየተባለ የሚመታበት ምክንያትም አይሁድ ኢየሱስን ሲመቱት ቀስ ቀስ እያሉና እያዘናጉ “አሁን ማነው የመታህ?” እያሉ ስለተዘባበቱበት እሱን ለማስታወስ ነው፡፡ ግራና ቀኝ የሚመታውም ምክንያት ክርስቶስን አይሁድ ሲመቱት በግራ በኩል ሲመቱት በተቃራኒው ሲያጎነብስ በቀኝ ሲመቱት በዚያው ተቃራኒ ሲያጎነብስ ያንን ለማስታወስ ሲሆን ከበሮ በትከሻ ተደርጎ ሲመታ ክርስቶስ ከወደቀበት አንስተው እንደመቱት ለማሳየት ነው፡፡

እንዲሁም መሰንቆን የወሰድን እንደሆነ፤ መሰንቆ አንድ ምሰሶና አንድ ክር ያለው የዜማ እቃ ነው፡፡ ክሩ ከፈረስ ጭራ ይዘጋጃል በአንድነት የሚወጠረው ክር ብዛቱ ቢያንስ አርባ ቢበዛ ሰማንያ ይሆናል፡፡ መሰንቆ ለእግዚአብሔር ክብር ይዘመርበታል፡፡ የመሰንቆ አንድ ምሰሶ መኖሩ ሃይማኖት አንድ መሆኑን፤ ክሩ አንድ ወራጅ መሆኑ አንዲት ጥምቀትን (ኤፌ 4፤5 አንዲት ጥምቀት አንዲት ሐይማኖት)፤ የክሩ ጥቅል ብዛት ቢያንስ አርባ መሆን ወንዶች በተወለዱ በአርባ ቀናቸው መጠመቃቸው፤ ቢበዛ ሰማንያ መሆኑ ሴቶች በሰማንያ ቀናቸው መጠመቃቸውን ያሳያል፤ ክሩ እጣን እየተቀባ ይዘመርበታል፤ ይህም ዕጣን የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው፡፡ ዛሬ ዋናው አላማዬ ስለ ሁሉም የዜማ እቃዎች ትንተና ለመስጠት አይደለም፡፡ ለመጠቃቀስ ያህል ለምን እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትን የዜማ መሳሪያዎች ብቻ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መጠቀም እንደፈለገች ለማሳየት ያህልና ሐይማኖት ውስጥ ያላቸውን አንድምታ ምን እንደሚመስል ለማሳየት ነው፡፡

 

ከመጻሕፍ ቅዱስ ማስረጃ በተጨማሪ ሌላ ቤተክርስቲያኗ ከመጻሕፍ ቅዱሱ ጋር አገናኝታና አሰናስና እንዴት እንደምትተረጉመው አይተናል፡፡ አሁን ለምን ኦርጋን አይፈቀድም ወደሚለው ጥያቄ እንመለሳለን፡፡ ኦርጋን በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም አይነት ማስረጃ የለውም (ይገባኛል መጻሕፍ ቅዱስ በተጻፈበት ጊዜ ስላልነበረ ነው የሚሉ አስተሳሰቦች ሊኖሩ ይችላሉ)፡፡ ኦርጋን መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ከሌለ ለምን ያስፈልጋል? ብዬ እኔ በተራዬ ብጠይቅስ፡፡ ለዜማ ትሉኝ ይሆናል? መልካም ለዜማ ከሆነ በገና፣ ከበሮ፣ ፅናፅል፣ መሰንቆ፣ ዋሽንት በቂ ነው ይላል የኦርቶዶክስ ቅዱስ ሲኖዶስ፡፡ እንደዚህ ከተባለ በእርግጠኝነት ሁለት መልስ መሰል ጥያቄዎች ይኖራሉ፡፡ አንደኛው “ምን ችግር አለው?” በኦርጋን ቢዘመር ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ወጣቶችን ለመሳብ፤ ዝማሬ በደንብና በሁሉ ውስጥ እንዲገባ ነው መልሱ፡፡ እነዚህን ነገሮች እናብራራቸው፡፡ “ምን ችግር አለው”ን እንየው፡፡ በአለም ላይ ክርስትናንም ሆነ ሌላውን ነገር ለጥፋትና ላልተፈለገ ውድቀት የዳረገው “ምን ችግር አለው” ነው፡፡ ዛሬ ምን ችግር አለው ተብሎ ኦርጋን ከተፈቀደ ይቀጥላል ምን ችግር አለው ፒያኖ፣ ክላርኔት፣ ሳክስፎን፣ ቫዮሊን፣ ዳንስ፣ በስሜት መወዛወዝ… ቢፈቀድ የሚሉ ጥያቄዎች ይመጣሉ፡፡ በመጀመሪያ በኦርጋን መዘመር ወይም አለመዘመር መዳንና ስለማዳን ማውራትም አይደለም፡፡

 

ስለዚህ ለወጣቶች እንዲህ ያለ ትንሽ አጀንዳ ሰጥቶ ማንጫጫቱን ለምን አስፈለገ? አዳኝ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ በክርስትና ትልቁ ጉዳይም የክርስቶስ ሰው መሆን የአምላክ በመስቀል ቀራንዮ ላይ መሰቀል እያለ፤ ኢየሱስ እልፍ አእላፍ ያደረገው ተአምር ከተአምርም በላይ ትልቅ የእመነት ጉዳይ ቁጭ ብሎ ኦርጋን እንዘምር አንዘምር ውስጥ እንኪያ ሰላምታ ስንገጥም የመዳን ጉዳይ ይረሳል፡፡ ኦርጋንን በመፍቀድ ወይም ባለመፍቀድ ኢየሱስ ክርስቶስን ሲዘነጋ ደግሞ ይቀጥላል ሌላ ረብ የለሽ አቧራ፡፡ ይህ ሁሉ አቧራ “በምን ችግር” አለው ሰበብ የመጣ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ የተረሱ ሰዎች፣ ትናንሽ ሀሳቦች፣ የማይጠቅሙ ጉዳዮች ቦታ ያገኛሉ፡፡ ሁለተኛው ለወጣቶች ተብሎ የሚደረግ ቤተክርስቲያንን የማዘመን ጉዳይ ነው፡፡ እውነት ይህ ጉዳይ ይሰራል? ዘለቄታዊ ጥቅምስ አለው? መልሱ ያለምንም ማወላዳት ምንም አይጠቅምም፤ ዘለቄታም የለውም፡፡ ማሳያ የሚሆነውም የአውሮፓውያንና የአሜሪካ ቤተእምነት ማየት ይቻላል፡፡ እነዚህ ቤተ እምነቶች ለወጣቶች ብላ ብዙ ዘመናዊና ለመጻሕፍ ቅዱስ ያልተመቹ ነገሮችን ፈቀደች ነገር ግን ወጣቶቿ ቤተክርስቲያኗ ውስጥ ለረጅም ጊዜ ሊቆዩላት አልቻሉም፡፡ ሀቁ ይህ ነው፡፡

 

ለዚህም ነው ቤተክርስቲያናቸውን ወደ ሙዚየምንት መቀየር የተገደዱት፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ኦርጋን ተፈቅዶ ያውቃልን? መልሱ ተፈቅዶ አያውቅም፡፡ ነገር ግን አራት ኪሎ ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን በኦርጋን መዘመርና ምስባክ ተጀምሮ ያውቃል፡፡ ኦርጋኑም እስከ ቅርብ ጊዜ ስላሴ ቤተክርስቲያን ውስጥ ነበር፡፡ ይህም የሆነው (ኦርጋኑን የተጠቀሙበት) በአቡን መርቆሬውስ የጵጵስና ዘመን በአቡነ መልከ ጼዴቅ የደብር አስተዳዳሪ በነበሩበት ጊዜ ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ዘማሪ ኪነጥበብ በኦርጋን የመዝሙር ካሴቶችንም አውጥቶም ያውቃል፡፡ ነገር ግን ዘማሪ ኪነጥበብ ከቤተክርስቲያኗ ልጆች ጥብቅ ተቃውሞ ደርሶበት ነበር፡፡ ስለዚህም ቀጣዮቹን መዝሙሮች በኦርጋን አልተጠቀመም፡፡ ከዚያም በ1986 ዓ.ም ግንቦት ወር ላይ በተደረገው የቅዱስ ሲኖዶሱ ጉባኤ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ያቀረበው የሰንበት ት/ቤቶች መመሪያ ጸድቋል፡፡ ከዚህ ውስጥም መዝሙር እንዴትና በማን ይዘመር የሚለውን በማያወላዳ መልኩ አስቀምጧል፡፡ እናም ቅዱስ ሲኖዶስ በተለይ በምን ይዘመር የሚለውን አንዲህ ሲል ያብራራል፡፡ “…በዋሽንት፣ በከበሮ፣ በጸናጽል፣ በመሰንቆ፣ በበገና፣ በእምቢልታ፣ በአርጋኖን (ኦርጋንና አርጋኖን ይለያያሉ) ብቻ እንዲጠቀሙ…” ያዝና እንዲህ የሚል ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፡፡ “…ከዚህ መመሪያ ወጥቶ በኦርጋን ልዘምር የሚል ካለ የቤተክርስቲያንቱ አባል አይደለም፡፡” ብሎ የማያወላዳ መልስ ሰጥቷል፡፡

እዚህ ውስጥ ክራር አለመኖሩን እናያለን ስለዚህም ክራር መጠቀም በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ክልክል ነው፡፡ “ነገር ግን ሁሉ በአግባብና በሥርአት ይሁን” 1ኛ ቆሮ 14፤40

The post በኦርጋን ቢዜም ምን ችግር አለው? (ቃልኪዳን ኃይሉ) appeared first on Zehabesha Amharic.

የአቶ ደብረጽዮንን ማስፈራሪያ ወደኋላ ያሉ የኦህዴድ ባለስልጣናት ከስልጣናቸው ሊነሱ ነው * ሙክታር ከድር ሊሰናበቱ ይችላሉ (ሪፖርታዥ)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ከጥቂት አመታት በፊት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር የኦህዴድ ባለስልጣናት ሲያስቸግሯቸው በፓርላማ ወጥተው “ባለስልጣናት ሃብታቸውን ማስመዝገብ አለባቸው” በሚል የጸረሙስና ክስ ሊመሰርቱ እንደሚችሉ ተናገሩ:: በወቅቱ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ አባዱላ ገመዳ ነበሩ:: አባዱላ በሙስና ልታሰር እችላለው በሚል መሸማቀቅ አዲስ አበባ ላይ በሙስና የሰሩትን ቭላ ቤት ለኢህ አዴግ ጽህፈት ቤት አስረከቡ::

File Photo

File Photo

ሰሞኑን ታሪክ ራሷን ደግሞ የኦሮሞ ሕዝብ ተቃውሞ በመላው ኦሮሚያ ሲናኝ አመጹን ለማስቆም የኦህ ዴድ ባለስልጣናት ምንም ሥራ አልሰሩም በሚል ሕወሃቶች በክፍተኛ ግምገማ ውስጥ ወድቀው ስንብተዋል ይላሉ የዘ-ሐበሻ ምንጮች:: አመጹ ከተቀጣጠለ በኋላ በኦህ ዴድ አመራር ላይ እምነት ያጡት ሕወሓቶች ልዩ አስተዳደር አቋቁመው ኦሮሚያን እየመሯት ይገኛሉ::

ከሁለት ሳምንት በፊት እነዚሁኑ የኦህዴድ ባለስልጣናት ለማስፈራራት የሕወሃቱ ቁልፍ ሰውና በጠቅላይ ሚኒስተር ማዕረግ ኢኮኖሚውንም ወታደሩንም የሚያዘው አቶ ደብረጽዮን ከመልካም አስተዳደር እና ከሙስና ጋር በተያያዘ የሚታሰሩ ባለስልጣናት እንደሚኖሩ በመንግስት ሚድያዎች ወጥቶ ተናገረ:: እንደዘ-ሐበሻ የውስጥ አዋቂ ምንጮች ይህ የአቶ ደብረጽዮን መግለጫ በቀጥታ የኦህዴድ ባለስልጣናትን ለምምታት ታልሞ ነው::

የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደሚሉት በተለይ የ ኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሙክታር ከድር ይህን የሕዝብ ቁጣ ለማብረድ የሰሩት ስራ ደካማ ነው እንደውም ከበስተጀርባው ይህን ሕዝባዊ ቁጣ ይደግፋሉ ወይም እንዲባባስ እየሰሩ ነው በሚል በሕወሓቶች ተወንጅለዋል:: ዛሬ ከጨፌ ኦሮሚያ ምክር ቤት ለዘ-ሐበሻ የመጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት የአቶ ሙክታር በስልጣን የመቆየት ነገር ያከተመለት ይመስላል:: ከቀናት በፊት አቶ ሙክታር ሃይለማርያም እና ከደመቀ መኮንን በመሩት የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ አለመገኘታቸውን የሚናገሩት የዘ-ሐበሻ ምንጮች ይህም በቀጣይ ኢላማ እርሳቸው መሆናቸውን ያሳያል ይላሉ::

በጨፌ ኦሮሚያ እየተገመገሙ የሚገኙት አቶ ሙክታር ከስልጣናቸው ተንስቶ በምትካቸው ሌላ ይሾማል ቢባልም እስካሁን ይህ ይፋ አልሆነም::

ሆኖም ግን ከኦህዴድ አካባቢ ያሉ ምንጮቻችን እንደሚሉት አቶ ደብረጽዮን በሚዲያ ወጥተው ካስፈራሩ በኋላም የሕዝቡ ቁጣ በማየል ላይ እንጂ በመብረድ ላይ ባለመሆኑ በርካታ የቀበሌና የወረዳ ጨምሮ ትንሽም ትልቅም ስልጣን ያላቸው የኦህዴድ ባለስልጣናት ተለቃቅመው በመታሰር ላይ ይገኛሉ::

ሕወሃቶች መለስ ከዚህ በፊት “ኦህዴዶች ፈጣን ሎተሪዎች ናቸው… ከላይ ሲታዩ ኦህዴድ ሲፋቁ ኦነግ ናቸው” የሚለውን በማንሳት ስልጣናችን ሳይነቃነቅ አሻንጉሊት መሪ በማስቀመጥ ክልሉን በቁጥጥራችን ስር ማዋል አለብን በሚል ሙሉ ስራቸውን ኦሮሚያ እና ኦህዴድ ላይ ማድረጋቸውን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አጋልጠዋል::

The post የአቶ ደብረጽዮንን ማስፈራሪያ ወደኋላ ያሉ የኦህዴድ ባለስልጣናት ከስልጣናቸው ሊነሱ ነው * ሙክታር ከድር ሊሰናበቱ ይችላሉ (ሪፖርታዥ) appeared first on Zehabesha Amharic.

ከማኅበረ ቅዱሳን ላይ እጃችሁን አንሱ –መልካም ሞላ

$
0
0

ፓትሪያሪክ አቡነ ማቲያስ ‹ማኅበረ ቅዱሳንን እዘጋለሁ› የሚለው ፉከራቸው በተሰማ በቀናት ውስጥ ይህን የሚገልጽ ደብዳቤ ከጽህፈት ቤታቸው ወጥቷል፡፡ ባለ ብዙ ገጽ ማብራሪያ ያለው ደብዳቤው የሚያትተው ስለማኅበረ ቅዱሳን ‹‹ ኃጥያት›› ቢሆንም እዉነታውን ለሚረዳ ግን ደብዳቤው በፓትሪያሪኩ ስም ይውጣ እንጂ የማን ፍላጎት አንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ እንዴት? ብሎ ለሚጠይቅ ደግሞ ደብዳቤው መጨረሻ ክፍል ላይ በግልባጭ እንዲደርሳቸው ተብለው የተጠቀሱት የመንግስት መስሪያ ቤት ዝርዝር ማየት በቂ ነው፡፡

ጋዜጠኛ መልካምሰላም ሞላ

ጋዜጠኛ መልካምሰላም ሞላ

ለጠቅላይ ሚነስትሩ፣ ለፌደራል ሚኒስቴር፣ ለአ.አ ፖሊስ ኮሚሽን፣ለፍትህ ሚኒስቴር፣ ለአዲስ አበባ ከንቲባ . . .ይልና መጨረሻ ላይ ትግራይ ክልላዊ መንግስት ርእሰ መስተዳድር፣ ለትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን እና ለትግ/መስ/ ፍትህ ቢሮ ይላል፡፡ በቅዱስ ሰኖዶስ ለሚተዳደር ቤተ-ክርስቲያን ከአዲስ አበባ እስከ መቀሌ ድረስ በግልባጭ የሚያሰጠው ለምን ይሆን? ማኅበረ ቅዱሳን ለእኔ በገባኝ እና ባወኩት እጅግ በጣም ባነሰ እውቀት ባጭሩ እንዲህ ፃፍኩት፡፡ እኔ ማኅበረ ቅዱሳንን ያወኩት የዩኒቨርስቲ ተማሪ እያለሁ ነው፡፡ ያኔ እኔ እና እኔን መሰል ጓደኞቼ ስለ ኃይማኖታችን የምናውቀው ነገር ቢኖር የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ መሆናችንን እንጂ ኃይማኖታችን ውስጥ ስላለው የከበረ ማእድን ጉዳይ እዉቀት አልነበረንም፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ገና ሀ ብለን ትምህርት ለመጀመር ግቢውን ስንረግጥ ጀምሮ በፍጹም ክርስቲያናዊ ፍቅር እንኳን ደህና መጣችሁ ብለው ተቀብለው አስተናግደውን ነበር፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ግቢው ውስጥ በቆየንባቸው 3 ተከታታይ አመታት ትምህርት ቀርፆ ስለኃይማኖታችን በሚገባ እንድናውቅ አድርጎናል፡፡ መሰረታዊ ትምህርት በመስጠት እግዚአብሔርን እያወቅነው እንድናመልከው ኃይማኖታችንን በማመን መታመን አጽንቶልናል፡፡ በወጣትነት ዘመናችን የዓለም ባህር ሳያሰጥመን በፊት መርከብ ሁኖ ወጀቡን አሳልፎናል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ነፍሳችንን አድኖታል፡፡ በመንፈሳዊም ይሁን በማህበራዊ ህይወታችን ፍቅርን መረዳዳትን እና መተሳሰብን . ወንድማዊ እና እህታዊ ግንኙነትን በዛ ከባድ በነበረው ዩኒቨርሲቲ ፤ በስጋ ብቻ ሳይሆን በነፍሳችን ተመርቀን እንድንወጣ አድርጎናል፡፡ ማኅበሩ በተመቻቸ ሁኔታ አልነበረም ያስተማረን፣ ቤት እስክናገኝ አንዲት ጠባብ ክፍል ግንድ አጋድመን ፣ መሬት ላይ ዘርግተን እየተቀመጥን፣ ቀን በትምህርት ሌሊት አዳር መርሃ ግብር እየተሰጠን ፣ እሁደ እሁድ በቤተክርስቲያን አዳራሽ ውስጥ (ያኔ ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ን ደሴ አላለቀም ነበር) ድንጋይና ግንድ ላይ ቁጭ ብለን ደስ እያለን እንድንማር ያደረገን እግዚአብሔርን እንድናውቅ ነፍሳችን ያተረፈልን ማኅበረ ቅዱሳን ነው፡፡ ማኅበሩ ህንፃ ለመግንባት ከማሰቡ በፊት መጀመሪያ የእኛን (በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚማሩ ተማሪዎችን) ልብ ውስጥ ፍቅረ እግዚአብሔርን ስሎ ህንጻውን ገንብቶ ነበር፡፡ ማኅበሩ አሁን እንዲህ ባማረ ህንፃ ከመቀመጡ በፊት አቧራ አራግፎ መሬት ላይ ቁጭ ብሎ ሰው ሲሰራ ነበር፡፡

ኃይማኖቴን ምን እንደሆነ ያወኩት በማኅበረ ቅዱሳን ነው፡፡ የሁሉም ህግ ማሰሪያ ስለሆነው ፍቅር በተግባር ያስተማረኝ ማኅበረ ቅዱሳን ነው፡፡ እኔ እና እኔን መሰል ብዙ እልፍ አእላፍ ነፍሳቶች በማኅበረ ቅዱሳን ተምረዋል፣ ብዙዎች ወደ ትክክለኛው መንገድ መጥተዋል፣ ብዙዎች ከጥፋት ጎዳና ተመልሰዋል፡፡ የዋና ማዕከል 5 ኪሎ ህንፃ መሰረቱ ድንጋይ ሳይሆን የማኅበሩ ፍሬዎች ልብ ነው፡፡ በአካቢያችን የነበሩ ራቅ ያሉ ጧፍ እና እጣን እንዲሁም ንዋየ ቅድሳት አጥተው ሊዘጉ የነበሩ ቤተ ክርስቲያኖችን ለቁርሳችን ያሰብነውን ዳቦ በመሸጥ እንዲከፈቱ ሲያደርጉ አይተናል፡፡ በማኅበሩ ቤተ-ክርስቲያን ከፍ ብላ ስትታይ አይተናል፡፡ የኢትዮጰያ ኦርቶዶክስን ቤ/ን ስርዓትን ጠንቅቀን እንድናውቅ ስላደረጉን የተሃድሶ ዜና አያስደነግጠንም፡፡ ዘፈን መሳይ መዝሙሮች አያሳስቱንም፡፡ ዛሬ አማኝ ሁነው ህዝቡን ሲያስጨበጭቡ የነበሩት ነገ ሌላ ዓላማ ይዘው ብቅ ሲሉ አይደንቀንም፡፡ የመናፍቃን ጩኸት አዲስ አይሆንም፤ እንጠነቀቃለን እንጂ በማዕበሉ አንነጠቅም፡፡ እግዚአብሔርን እንጂ ሰው ሰለማንከተል ታዋቂ አጥማቂ ፣ታዋቂ ሰባኪ ፣ታዋቂ . . . የሚሉት ዘመን አመጣሽ ግርግሮች አያናውጡንም፡፡

እግዚአብሔር ድንቅን ይሰራል እናምናለን፤ በሃሰተኞች ግን አንታለልም፡፡ ምክንያቱም ስለኃይማኖታችን ከማስረጃ ጋር ጠንቅን እንድናውቅ አስተምረውናል፡፡ ይሄ በጥቂት አመታት በወሎ ዩኒቨርሲቲ ለሶስት ዓመት ያየሁት ስራ ነው፡፡ ብጹዕ ፓትሪያሪኩ ማኅበሩ ለምን እንደሚያሰጋቸው አልገባኝም፡፡ ምናልባትም ከቤተ ክህነት በተሻለ መንገድ እየተንቀሳቀሰ ስለሆነ ይሆናል፡፡ሌላው በሙስና የተጨማለቁት የውስጥ ሰዎች እንዳይጋለጡም ይሰጋሉ፡፡ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በፓርላማ በአክራሪነት ፈርጀውት ነበር፡፡ ራዕያቸውን እያስቀጠሉ ያሉት ዛሬም እየለፉ ናቸው፤ለማፍረስ፡፡ ዛሬም በአንድም በሌላም መንገድ ማኅበሩን ለማዳከም ፈተናዎች ብዙ ናቸው፡፡ ከሁለት አመት በፊት ስለማህበራት በተመለከተ አዋጅ ሊፀድቅ ተብሎ( ስራ ላይ ይዋል አይዋል አላውቅም) በተጠራው ስብሰባ ላይ እሰራበት የነበረውን መጽሄት ወክየ ተገኝቼ ነበር፡፡ ባጭሩ አዲስ ይወጣል የተባለው ደንብ ማንኛውም ማህበር ምንም አይነት የልማት ስራ መስራት አይችልም የሚል ይዘት ያለው ነው፡፡ አዋጁ በቀጥታ ለማህበረ ቅዱሳን መምቻ ተብሎ እንደወጣ ግልጽ ነበር፡፡ እኛ በማናውቃቸው የማህበሩ አመራሮች እና ሰራተኞች የሚያውቋቸው እጅግ ብዙ ፈተናዎች እየደረሰበትም የእግዚአብሔር ፍቃድ ስለሆነ እና ስለወደደው እስካሁን በጽናት ቆሟል፡፡

ዛሬም የወጣው ደብዳቤ ለማኅበሩ አዲስ ፈተና አይደለም፡ የሚገርመው ግን መናፍቃን እና ተሃድሶዎች በውስጥ እና በውጭ ሊያፈርሱ ሲተጉ መንግስት አይኑን ተክሎ ሊያጠፋው እየጠበቀ የቤተክርስቲያኗ የበላይ ጠባቂ በተቃራኒ ጎን መቆሙ ብቻ ነው፡፡ እዉነት ነው ማኅበረ ቅዱሳን እንኳን መንግስትን ቤተ ክህነትን ያስደነግጣል፤ ምክንያቱም ስሙን ይዞ የተኛውን ቤተ ክህነት ስራ ተቀብሎ ማኅበሩ እየሰራ ነው፡፡ ሰነፍ እረኛ የእሱን ከብቶች ጅብ ስለበላቸው ሳይሆን ነቅቶ የጠበቀው ባልጀራው ከብቶች ስለበዙ ይናደዳል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን የአብነት ተማሪዎችና ገዳማት ራሳቸው እንዲችሉ የሚያስችል እቅድ ነድፎ ይንቀሳቀሳል እንጂ ሌላ ድብቅ አላማው የለውም፡፡ ቃለ ወንጌል ባልተስፋፋባቸው ቦታዎች በተለያዩ ቋንቋዎች መምህር አሰልጥኖ በማስማር እጅግ ብዙ ክርስቲያኖች አስጠምቋል፡ ክርስትናን አስፋፍቷል፡፡ ቤተክህነቱ ወይም ሲኖዶሱ የረሳቸውን ገዳማት የተዘጉ ቤተክርስቲያኖች ፣ የአብነት ተማሪዎች እየረዳ በሁለት እግራቸው አቁሟቸዋል እንጂ ‹ለድብቅ › አላማ አልተጠቀመባቸው፡፡ በመሰረቱ ይህች ቃል ከየት እንደመጣች ትታወቃለች፡፡ ቴሌቭዥናችን አስሬ እየመጣ አክራሪ እያለ ሲያደነቁረን ከርሟል፡፡

ማኅበሩ ባለ ሁለት ዲጅት የሂሳብ ሲስተም የሚጠቀም እንጂ እንደ አብዛኞች ቤተክርስቲያኖች ለሙስና የሚያጋልጥ አሰራር የለውም፡፡ እቅዱም በአመቱ መጀመሪያ (በቤተክህነት?) አጸድቆ ይጀምራል ኦዲት ተደርጎ ይታያል፡፡ ገዳማትን ሲረዳ፣ ጤናቸው እንዲጠበቅ ተወካዮችን እየሰበሰበ ትምህርት ሲሰጥ ፣ በየገጠሩ እየዞረ ሲያስተምር እንጂ በሚሊዮን ዶላር መኪና ሲገዛ ፤የቤት እቃ ‹ሰርፕራይዝ › እያለ ሲያሟላ አላየንም ፤አልሰማንም፡፡ ለመሆኑ ሲኖዶሱ ዋልድባ ሲታረስ መግለጫ አውጥቶ ነበር? ቆብ አጥልቀው በሃሰት እያስተማሩ እያጠመቁ ብዙ መቶ ሺዎች ክርስቲያኖች ግራ ግቷቸው ሲባዝኑ ያለው ነገር ነበር? ያሬዳዊ ዜማን የለቀቀ እና ዝላይ የበዛበት መዝሙር እና ለዛ ቢስ ስብከት እየተመረተ ምእመናኑ ሲዋትት ምን ብለው መግለጫ አውጥተው ነበር? ምን ብለው እርምጃ ወሰዱ? ወጣቱን የታደገው ማነው? እነ ብጹዕ አቡነ ተክለኃይማኖት እና አቡነ ቴዎፍሎስ ወንበር ላይ ተቀምጦ የመጣን ደብዳቤው ፈርሞ ማውጣት በእዉነት አይከብድም? እርግጥ ነው ህንጻው ይፈርስ ይሆናል፡፡ ግን ልባችን የበቀለውን ፍሬ እንዴት ማጥፋት ይቻልዎታል? በነገራችን ላይ በቅዱስ ሲኖዶስም ይሁን በቤተክህነት ውስጥ እጅግ ለማኅበሩ የሚቆረቆሩ እና የሚጠብቁት፣ የሚጸልዩ ብፁዓን አባቶች አሉ፡፡ ያስቸገሩት ከላይ እየታዘዙ የሚያስፈጽሙ ጥቂቶች ናቸው፡፡ የጽሁፍ መደምደሚያ ግን አንድ እና አንድ ነው፡፡ መንግስት ከማህበሩ ላይ እጁን ያንሳ፡፡

እደግመዋለሁ ደብዳቤው በፓትሪያሪኩ ተፈርሞ ይውጣ እንጂ ከኋላ እጅ ጠምዝዘው የሚያጽፉት እነማን እንደሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ከማኅበሩ ላይ እጃችሁን አንሱ፡፡

The post ከማኅበረ ቅዱሳን ላይ እጃችሁን አንሱ – መልካም ሞላ appeared first on Zehabesha Amharic.

የአጋዚ ሰራዊት ኢትዮጵያውያኑን በሱሉልታ ሲያሰቃይ የሚያሳይ እጅግ አሰቃቂና አስነዋሪ ቪድዮ

$
0
0

የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ የአጋዚ ሰራዊት ኢትዮጵያውያኑን በሱሉልታ ሲያሰቃይ የሚያሳይ እጅግ አሰቃቂና አስነዋሪ ቪድዮ ለቆታል:: ይመልከቱት:: ላላዩት በማሳየት የዚህን አረመኔ ሥርዓት ድርጊት ያጋልጡ::

The post የአጋዚ ሰራዊት ኢትዮጵያውያኑን በሱሉልታ ሲያሰቃይ የሚያሳይ እጅግ አሰቃቂና አስነዋሪ ቪድዮ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢሳት:-ጋምቤላ ክልል በፌደራል መንግስት ቁጥጥር ስር ወደቀች።


በጆርጃ –አትላንታ እና አካባቢው ያላችሁ ኢትዮጵያውያን ጥሪ ቀርቦላችኋል

ቴዲ አፍሮ እና አብይ ላቀው ለኮራ የሙዚቃ አዋርድ ታጭተዋል |የሁላችንንም ድምጽ ይፈልጋሉ –እንምረጥ

$
0
0

teddy afro and abby Lakew

(ዘ-ሐበሻ) አድናቂዎቹ የፍቅር ንጉሥ እያሉ የሚያሞካሹት ድምፃዊው ቴዲ አፍሮ እና በ ቅርቡ እንደገና ‘የኔ ሐበሻ’ አዲስ ነጠላ ዜማዋን የለቀቀችው ድምፃዊት አብይ ላቀው ለታዋቂው የኮራ የሙዚቃ አዋርድ እጩ ሆነው ቀረቡ:: ሁለቱ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች ለዚህ ክብር የበቁት ሃገራችን ኢትዮጵያን ወክለው በመሆኑ የሁላችንም ድምጽ አስፈላጊ ነው::

የሌሎች ሃገራት ሕዝቦች የራሳቸው አርቲስት እንዲመረጥ ቅስቀሳ ከማድረግም በላይ በመምረጥም ላይ ይገኛሉ:: ከጃንዋሪ 20, 2016 ጀምሮ ለሕዝብ ይፋ የሆነውና ሕዝቡም በመምረጥ ላይ የሚገኝበት ይኸው የኮራ አዋርድ ቴዲ አፍሮን በምርጥ ዝነኛ ድምጻዊ (LEGENDARY AWARD) የውድድር ካታጎሪ እንዲሁም አብይ ላቀውን በምርጥ የሴት የባህል ድምፃዊነት (Best Traditional Female Artist) ካታጎሪ አብይ ላቀው ታጭተዋል::

የኮራ አዋርድ ከ55 ቀናት በኋላ አሸናፊዎች የሚታወቁ ሲሆን ከዚያ በፊት ግን ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያውያን ወዳጆች ለሁለቱ ድምጻውያን በጽሁፍ መልዕክት ድምፃቸውን መስጠት ይችላሉ::

+248984000 ስልክ ቁጥሩ ሲሆን ለአብይ ላቀው KORA 74 የሚለውን ቴክስት በማድረግ መምረጥ ይቻላል::
እንዲሁም ለቴዲ አፍሮ በተጠቀሰው ስልክ ቁጥር KORA 156 በማለት ቴክስት በማድረግ መምረጥ ይቻላል:: አስታውሱ ለሁለቱም ድምፃውያን ድምጽ መስጠት ይቻላል – የዜግነት ግዴታዎን ይወጡ::

INTERNATIONAL VOTING, SMS YOUR ARTIST’S VOTING CODE TO +248984000

Teddy Afro: KORA 156

Abby Lakew: KORA 74

ለበለጠ መረጃ እንዴት መምረጥ እንደሚችሉ ለማወቅ
http://www.koraawards.com/en/news/how-to-vote-for-your-favourite-artists/#prettyPhoto

The post ቴዲ አፍሮ እና አብይ ላቀው ለኮራ የሙዚቃ አዋርድ ታጭተዋል | የሁላችንንም ድምጽ ይፈልጋሉ – እንምረጥ appeared first on Zehabesha Amharic.

በሾላ ገበያ የእሳት አደጋ ተነስቶ ሱቆች ነደዱ |አጭር የቃጠሎውን ቪዲዮ ይዘናል

$
0
0


(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ በተለምዶ ስሙ ሾላ ገበያ በሚባለው አካባቢ ዛሬ እኩለ ቀን አካባቢ በተነሳ ቃጠሎ ሱቆች መንደዳቸው ተሰማ:: እንደ ዘ-ሐበሻ የአዲስ አበባ ዘጋቢዎች ከሆነ በሾላ ገበያ ፍራሽ ተራ አካባቢ ሱቆች በቃጠሎው ነደዋል::

በተለይ ፍራሽ ተራ አካባቢ ያሉ አንዳንድ እሳቱን ሊያባብሱ የሚችሉ ነገሮች ለ እሳቱ መስፋፋት አስተዋጽኦ ቢያደርጉም የአካባቢው ነዋሪም እሳቱን ሊያባብሱ የሚችሉ አንዳንድ እቃዎች ሲያሸሽ እንደነበር ገልጸዋል:: የአዲስ አበባ እሳት አደጋ ሱቆች ከነደዱ በኋላ አደጋው እንዳይስፋፋ የማጥፋት ሥራ እንደሰራ የሚገልጹት የዓይን እማኞች በሰው እና በሕይወት ላይ ጉዳት ስለመድረሱ ማስረጃ እንዳላገኙ ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል::

በሾላ ገበያ ፍራሽ ተራ አካባቢ የተነሳው ቃጠሎ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ንብረቶችን ቢያወድምም ትክክለኛው ቁጥር ግን አልታወቀም::

የዚህ የእሳት ቃጠሎ መነሻ አልታወቀም:: ሆኖም ግን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት አመራሮች ከዚህ ቀደም በተለያዩ ቦታዎች ሊያስነሳቸውና ለሌላ ሰው ቦታውን ሊሸጠው የሚፈልገውን ቦታ የ እሳት አደጋ በማስነሳት ወንጀል ሲወነጀሉ መቆየታቸው ይታወሳል::
shola

The post በሾላ ገበያ የእሳት አደጋ ተነስቶ ሱቆች ነደዱ | አጭር የቃጠሎውን ቪዲዮ ይዘናል appeared first on Zehabesha Amharic.

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት:- ፀረ-ወያኔ አቋም ለአላቸው የኢትዮጵያውያን የፖለቲካ፣ የሲቪክ እና የሙያ ማኅበራት በሙሉ –መነሻ የመግባቢያ ኃሣብ ስለማቅረብ

$
0
0

ሐሙስ ጥር ፲፱ ቀን ፪ሺህ፰ ዓ.ም. (Thursday January 28, 2016)                                                                

ሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት፣ 

 ፀረ-ወያኔ አቋም ለአላቸው የኢትዮጵያውያን የፖለቲካ፣ የሲቪክ እና የሙያ ማኅበራት በሙሉ

በያሉበት

 

ጉዳዩ፦ መነሻ የመግባቢያ ኃሣብ ስለማቅረብ፦ እስከ አንድነት ለመድረስ የሚያስችል ውጤታማ ትብብር ለማድረግ መከተል ስለሚገባን አካሄድ፤ 

 moresh

ማናችንም እንደምንገነዘበው፣ ባለፉት 40 እና 50 ዓመታት ኢትዮጵያውያን ስንደራጅ የኖርነው በልዩነቶቻችን ላይ ባተኮሩ ዓላማዎች ዙሪያ ነው።ልዩነቶቻችን ደግሞ ከርዕዮተ-ዓለም ባሻገር፣ በነገድ፣ በጎጥ እና በኃይማኖት ጭምር ያጠነጠኑ በመሆናቸው፣ አንድነታችንን አሳሳቢ ደረጃ ላይ አድርሶታል። ከሁሉም በላይ፣ የትግሬ-ወያኔ በባዕዳን ድጋፍ ተበረታትቶ፣ ግንቦት 20 ቀን 1983 ዓ.ም. የፖለቲካ ሥልጣን ሲጨብጥ፣ ያስተጋባው የዲሞክራሲ ቀቢፀ-ተስፋ እውነት መስሏቸው የተከተሉት ወገኖች አይጠፉም። ሆኖም ይህ ፀረ-ኢትዮጵያ ቡድን በተግባር ሲያከናውን የሚታየው፥ የቋንቋ ፣ የነገድ ፣ የጎሣ ፣ የዘር ፣ የኃይማኖት ፣ ወዘተርፈ ልዩነቶችን መሠረት አድርጎ ሕዝቡ ለዘመናት ገንብቶት በኖረው ኢትዮጵያዊ ማንነት ላይ ግልጽ የጥፋት ዘመቻ ማካሄድን ነው። የትግሬ-ወያኔ ባለፉት 25 ዓመታት ውስጥ በአካሄደው የዘር ልዩነት ፖለቲካ ግፊት፣ ሕዝቡ ኢትዮጵያዊ ማንነቱን ችላ እያለ፣ በቋንቋ ማንነቱ ዙሪያ ብቻ እንዲያስብ እና እንዲደራጅ አድርጓል። በዚህም ምክንያት ለሕዝቡ አንድነት ጌጥ እና ውበት፣ ጥንካሬ እና ልዩ መታወቂያ የሆኑት ነባራዊ ልዩነቶች የጠብ እና የብጥብጥ መነሻዎች ሆነዋል። በዚህ ረገድ የአያሌ ዜጎች ሕይዎት መጥፋቱን፣ ንብረት መውደሙን እናውቃለን። በተለይም ኢትዮጵያውያን ዐማሮች የአማርኛ ቋንቋ በመናገራቸው ብቻ ለዘመናት ከኖሩበት አካባቢ ተለይተው ሀብት ንብረታቸውን እየተዘረፉ መባረራቸውን ማስታወስ ይበቃል።  በዐማራ፣ በአኙዋክ ፣ በሶማሌ እና በሌሎች ነገዶች ተወላጆች ላይ የሚደርሰው የዘር ማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ወንጀል ሊገታ አለመቻሉ  የአደባባይ ምስጢር ነው። ስለዚህ ይህ ድርጊት እየተባባሰ በመሄድ ላይ ስለሆነ፣ አፋጣኝ እና መሠረታዊ መፍትሔ የሚሻ ጉዳይ ነው።

የትግሬ ወያኔው አገዛዝ በሥልጣን ላይ ሊቆይ የሚችለው፣ ፍትሐዊ አስተዳደርን በማራመድ ሳይሆን፣ የጀመረውን  የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲውን እያራቀቀ በመሄድ ብቻ መሆኑ ከእንግዲህ ሊያጠያይቅአይችልም። ስለሆነም፣ ይህን  የትግሬ ወያኔውን አገዛዝ በጠመንጃ ኃይል ከጨበጠው የፖለቲካ ሥልጣን በእርግጠኝነት በማላቀቅ አሽቀንጥሮ  ለመጣል ከኢትዮጵያውያን አንድነት የተሻለ አስተማማኝ መሣሪያ አይኖርም። ለዚህ ደግሞ፣ እስካሁን የተጓዝንበትን የልዩነት ጉዞ መተው፣  በኢትዮጵያዊነት አገራዊ ስሜት በአንድነት መቆም ያስፈልጋል። ስለሆነም ከልዩነቶቻችን ይልቅ በአንድነታችን ላይ አትኩረን በኅብረት መንቀሳቀስ አማራጭ አይኖረውም  አንድነት ኃይል ነው፤ ጥንካሬ ነው፤ የማድረግ ብቃት ማረጋገጫ ነው።

 ሰሞኑን ከየአቅጣጫው የሚሰሙት የ«እንተባበር» እና የ«አንድነት» ጥሪዎች ወቅታዊ ስለሆኑ አዎንታዊ ምላሽ ሊያገኙ ይገባል። ለተግባራዊነታቸው አስተማማኝ መሠረት ለመጣል ደግሞ፣  «በኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል» የሚሉ ወገኖችን ሁሉ አካትቶ፣ ለሚታሰበው አንድነት ጉዞ ፈር ቀዳጅ የሆነ የምክክር መድረክ ይዋል ይደር ሳይባል መፈጠር ይኖርበታል። ለዚህ ሂደት ውጤታማነት ተሞክረው ለግብ ካልበቁ የስምምነት ሙከራዎች ትምህርት ሊቀሰም ይገባል። እንዳለፉት ስምምነቶች ሁሉ የተፈረመባቸው ቀለም ሳይደርቅ ወደ ነበሩበት የመመለስ ሁኔታ እንዳይገጥም፣ የተስማሚ ወገኖችን ይሁንታ ያገኘ የመግባቢያ ሰነድ ሊዘጋጅ ይገባል። ይህ ሰነድ ወደ ዋናዎቹ የስምምነት ጉዳዮች ለመግባት ተስማሚዎቹ ወገኖች አምነውና ዐውቀው፣ የውዴታ ግዴታ የሚገቡበት አስገዳጅ እና ተፈጻሚነት ያለው ይዘት ሊኖረው ይገባል። ሰነዱ ከተዘጋጀ እና ሁሉም አንድነት ፈላጊዎች ተስማምተው ከፈረሙበት በኋላ፣ ለሕዝብ ይፋ ሆኖ ሂደቱን ሕዝቡ በባለቤትነት እንዲከታተለው እና ተስማሚ ወገኖችም የተጠያቂነትና የኃላፊነት ስሜት እንዲያድርባቸው  ማድረግ ይገባል። 

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት አገራችን ኢትዮጵያ የገባችበትን አሳሳቢ ሁኔታ በመግለጽ እና በአስቸኳይ ቢወሰድ አደጋውን ሊያስወግድ ይችላል ብሎ ያመነበትን የመፍትሔ ኃሣብ በመጠቆም ከዚህ በላይ የሰፈረውን አቅርቧል። ለአፈጻጸም ይረዳ ዘንድም፣ ከዚህ በታች የተመለከቱት አስፈላጊ እርምጃዎች በውል እየተጤኑ ተግባራዊ እንዲሆኑ ያሳስባል።

1.         ስምምነቱን የሚመራ ኮሚቴ ሊመሠርት የሚችል የጋራ መድረክ መፍጠር

(ሀ)        ይህ መድረክ ከአንድ ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ መጠራት ይኖርበታል። 

(ለ)        መድረኩ ኃላፊነት በወሰዱ ወይም በሚወስዱ ድርጅቶች አማካኝነት ይጠራል።  

(ሐ)       ለመድረኩ እያንዳንዱ በኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ የፖለቲካ፣ የሲቪክ ና የሙያ ማኅበራት በአምስት በአምስት ሰዎች ይወከላሉ፤ ታዋቂ ግለሰቦች እና የኃይማኖት ድርጅቶች እያንዳንዳቸው በአንድ  ሰው የሚወከሉ ይሆናል።

(መ)       የመድረኩ ኃላፊነትም ለቀረበው የአንድነት ጥሪ አዎንታዊ መልስ ለመስጠት የሚያስችል አስማሚ ኮሚቴ መመሥረት እና አስማሚ ኮሚቴው ሊያተኩርባቸው በሚገባቸው የመግባቢያ ሰነዶች ይዘት ላይ ለመወሰን ይሆናል።

2          የአስማሚ ኮሚቴ አባሎች አመራረጥ

(ሀ)        በተዘጋጀው መድረክ በተገኙ አባሎች አማካኝነት በሚደረግ ውይይት ቁጥራቸው ከአሥራ አምስት እስከ ሃያ አንድ የሚሆኑ የኮሚቴ አባሎችን የያዘ ኮሚቴ መመሥረት ።  

(ለ)        የኮሚቴ አባላቱም ከሚከተሉት አንዱን ወይም ከሁሉም በማቀላቀል መመሥረት ይቻላል። 

3        የኮሚቴው አባላት ይዘት

(ሀ)        በሁሉም ተስማሚዎች አመኔታና አክብሮት የተቸራቸው ታዋቂ ኢትዮጵያውያን ግለሰቦች፣ 

(ለ)        በኢትዮጵያ ካሉት ነገዶች እና ጎሣዎች ከአምስት መቶ ሺህ ሕዝብ በላይ ያላቸው የነገድ እና የጎሳ ተወካዮች፤

(ሐ)       ከኢትዮጵያ ታላላቅ ኃይማኖቶች ታዋቂ አባቶች ፤፤ 

 

4        የቴክኒክ የሥራ ቡድን ስለ ማቋቋም

(ሀ)        ለሚቋቋመው አስማሚ ኮሚቴ ሥራ መቃናት እና መቀላጠፍ የሚያግዙ በሁሉም ተስማሚ ወገኖች ይሁንታ ያገኙ፣ ወይም ከተስማሚ ወገኖች ተመጣጣኝ ውክልና ያላቸው የቴክኒክ የሥራ ቡድኖች መቋቋም አለባቸው።

(ለ)        የእነዚህ የሥራ ቡድኖች ተግባርና ኃላፊነታነታው በግልጽ የሰፈረ፣ ከአስማሚ ኮሚቴው ጋር ሊኖራቸው የሚችለው የሥራ ግንኙነት በማያሻማ መንገድ የተገለጸ መሆን ይኖርበታል። 

5          የኮሚቴው የሥራ ጊዜ እና የአፈጻጸም ጉዳዮች

(ሀ)        አስማሚ ኮሚቴው በሥራ ላይ የሚቆይበት ጊዜ የተወሰነ መሆን ይኖርበታል። 

(ለ)        ኮሚቴው ዝርዝር የሥራ አፈጻጸም መመሪያዎችን ያዘጋጃል።

(ሐ)       ኮሚቴው የተሳታፊ ድርጅቶችን እና ና ግለሰቦችን አመራረጥ መስፈርት ያዘጋጃል።

(መ)       የስምምነቱ ሥነሥርዓት የሚገዛበት ደንብ እና  የአሠራር ቅደም ተከተል መመሪያዎች በኮሚቴው ይዘጋጃሉ።     

6          ትኩረት የሚጠይቁ ሌሎች ጉዳዮች

(ሀ)        ተስማሚዎቹ ወገኖች ከስምምነት ከደረሱ በኋላ ማከናወን ያለባቸውን አንኳር አገራዊ ጉዳዮችን ለይቶ ማስቀመጥ፣

(ለ)        ከወያኔ ውድቀት በኋላ ኢትዮጵያ ልትከተለው ስለሚገባ የአስተዳደር እና የፖለቲካ ሥርዓት በአገር አንድነት ከተስማሙ ወገኖች  የቀረቡ ኃሣቦችን  ማቀናጀት፤

(ሐ)       ስምምነቱ የሚካሄድበት አገር፣ ከተማ እና ጊዜ መወሰን፤

(መ)       በመግባቢያ ሰነዱ የተስማሙ ድርጅቶችን፣ ቡድኖችን፣ ስብስቦችን እና ማኅበሮችን ማንነትና የሚወክሏቸውን ሰዎች ማንነት ለይቶ መመዝገብ፤

(ሠ)       የስምምነቱ ሂደት እና ውጤት የሚገለጽባቸውን ቋንቋዎች መወሰን፤

(ረ)        ስምምነቱ በሚገለጽባቸው ቋንቋዎች መካከል የትርጉም ልዩነት ቢከሰት፣ በዋናነት የሚወሰደውን ቋንቋ ለይቶ መወሰን፤

7            ተጨማሪ ማሳሰቢያ

(ሀ)        አንድነት የሚፈጥሩ ቡድኖች የሚለያዩባቸው አቋሞች ቢኖሯቸውም የአገር አንድነትን በተመለከተ የሚጋሯቸው እሴቶች ምን እንደሆኑ ተለይተው መቀመጥ ይኖርባቸዋል።

(ለ)        በመስማሚያው ወይም መግባቢያው ሰነዱ እና በአሠራሩም ቅደም ተከተል ስምምነት ከተደረገ በኋላ፣ ወደ ዋናው ጉዳይ ሲገባ፣ ስምምነቱ በቀና እና በታሰበው ጊዜ እንዲከናወን፣ ተሳታፊዎች «አሉኝ» የሚሏቸውን የአቋም ጥያቄዎች በክብደታቸው ቅደም ተከተል መሠረት አስማሚው ኮሚቴው በሚወስነው የጊዜ ገደብ ውስጥ በጽሑፍ እንዲያቀርቡ ማድረግ ሥራን ያቀላጥፋል። ከዚህ በተጨማሪ ስምምነቱም በእነዚያ ነጥቦች ዙሪያ ብቻ እንዲያተኩር መወሰኑ በውይይቱ ወቅት ሰጥቶ ለመቀበልም ሆነ፣ «ይህ ካልሆነ» ብሎ አቋምን አጠንክሮ ለመጓዝ ይረዳል።

እነዚህና መሰል ጉዳዮችን የሚያካትት ሰነድ መዘጋጀት ለሚታሰበው አንድነትና የትብብር ጥሪ ውጤታማነት ያገለግላል ብሎ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ያምናል።

The post ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት:- ፀረ-ወያኔ አቋም ለአላቸው የኢትዮጵያውያን የፖለቲካ፣ የሲቪክ እና የሙያ ማኅበራት በሙሉ – መነሻ የመግባቢያ ኃሣብ ስለማቅረብ appeared first on Zehabesha Amharic.

“ለጋዜጣ ጉዳዩን ማቅረብ የተፈለገው ከቀናነት በመነጨ ሳይሆን፤ በማር የተለወሰ መርዝ ነው” –አቶ አበራ ገብሩ

$
0
0

ሰንደቅ

ባሳለፍነው ሳምንት የሰማያዊ ፓርቲ የዲስፒሊን ኮሚቴ አንድ ሥራአስፈፃሚ እና በሶስት የምክር ቤት አባላት ላይ ያስተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም የፓርቲው ሥራአስፈፃሚ መግለጫ ማውጣቱ የሚብስ ነው። ይህንንም ተከትሎ የኦዲትና የምርመራ ኮሚሽን የመጨረሻ ውሳኔ እየተጠበቀ መሆንም መዘገባችን ይታወቃል።

ዝግጅት ክፍላችንም የሰማያዊ ፓርቲ የኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን ሰብሳቢ የሆኑትን አቶ አበራ ገብሩ አነጋግረናቸዋል። ከሳቸው ጋር ያደረግነው ሰፋ ያለ ቃለ ምልልስን በዚህ መልኩ አቅርበነዋል።

ሰንደቅ፡- ባለፈው ሳምንት የፓርቲያችሁ ሥራአስፈፃሚ የዲሲፕሊን እርምጃ የተወሰደባቸውን አራት አባላት ውሳኔ እንደማይቀበል በይፋ አስታውቋል። በእነዚህ ሁለት አካላት የተፈጠረውን አለመግባባት ኦዲትና ምርመራ ኮሚሽኑ ለመፍታት ምን እያደረገ ይገኛል?

አቶ አበራ፡- በመጀመሪያ ደረጃ በዚሁ ጋዜጣ ላይ የኦዲትና ምርመራ ኮሚሽኑ ውሳኔ እየተጠበቀ ነው በሚል የዘገባችሁት ዜና መነሻውን እናንተ ብቻ ነው የምታውቁት። መታወቅ ያለበት በአሁን ሰዓት ኦዲት ኮሚሽኑ እየተመለከተው የሚገኝ የይግባኝ አንዳችም ጥያቄ የለም። ይህ በሆነበት ሁኔታ ምንድን ነው እኛ የምንመለከተው።

ሰንደቅ፡- በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሰረት ሥራአስፈፃሚው እና በምክር ቤቱ መካከል ልዩነቶች ሲፈጠሩ የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጠው ኦዲትና ምርመራ ኮሚሽኑ መሆኑን ይደነግጋል። ስለዚህም ሥራአስፈፃሚው የዲሲፕሊን ኮሚቴውን ውሳኔ ውድቅ ማድረጉ እና የምክር ቤቱን የክስ ይዘት አልቀበልም ማለቱን የኦዲትና ምርመራ ኮሚሽኑ ይግባይ ስላልቀረበለት ብቻ በዝምታ ያልፈዋል ማለት ነው?

አቶ አበራ፡- ሥራ አስፈፃሚው በማያገባውና በማይመለከተው ሥልጣን እና ተግባር ውስጥ ነው የተዘፈቀው። ምክንያቱም ሥራአስፈፃሚው ከሳሽም ተከሳሽም ባልሆነበት ሁኔታ ከሳሽም ተከሳሽም ራሳቸውን መከላከል በሚችሉበት ሁኔታ ውሳኔውን ተቀባይም ነሺም የሆነበት መንገድ ሕገወጥ ነው። በደንባችን መሰረት የዲሲፕሊን ኮሚቴ ውሳኔ የመጨረሻ ውሳኔ ተደርጎ የሚወሰድ አይደለም። የይግባኝ አቀራረብ ደንብና ስርዓት በፓርቲው ውስጥ አለ። ይህ ሕጋዊ መስመር ብቻ ነው የተፈጠሩ የውሳኔ ልዩነቶች መመልከት የሚችለው። ከዚህ ውጪ ያለው አካሄድ በሕግም በሌላም መመዘኛ ተቀባይነት የለውም።

እዚህ ላይ ግልፅ መሆን ያለበት የኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን የዲሲፕሊን ኮሚቴውን ውሳኔ የማየት ስልጣን ብቻ ሳይሆን አስፈላጊ ነው ብሎ ካመነ በፓርቲው በየትኛውም መዋቅር ስር የሚገኙ ሰነዶችን ጠይቆ ምርመራ የማካሄድ ስልጣን አለው። ስለዚህም ሥራአስፈፃሚው በዲሲፕሊን ኮሚቴው አካሄዶች እና በክሱ ይዘት ቅሬታዎች አለኝ ቢል እንኳን ለኮሚሽኑ ጥያቄውን ማቅረብ ይችል ነበር። ምክንያቱን በማናውቀው መንገድ ይህን ሕገወጥ መንገድ ለምን እንደመረጡ ግን አልገባንም።

ሰንደቅ፡– እርስዎ ያሉት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በአሁን ሰዓት በፓርቲው ውስጥ የተፈጠረ ልዩነት መኖሩ የአደባባይ እውነት ነው። ይህ በሆነበት ሁኔታ ይግባኝ አልቀረበልንም በሚል ምክንያት ብቻ ጉዳዩን አቅርቦ አለመመልከት ከኃላፊነት መሸሸ ወይም በቀጣይ ሊያስጠይቃችሁ የሚችል ነገር አይኖርም ብሎ መውሰድ ይቻላል?

አቶ አበራ፡- መጠንቀቅ ያለብን እየተባለ ያለው ወይም ከሕግ አግባብ ውጪ ለአደባባይ የቀረበው ነገር ምን ያህል እውነትነት አለው? ይህንን ጥያቄ መመለስ ስንችል ነው ፓርቲው ውስጥ ችግር አለ ወይም የለም ለሚለው ምላሽ የሚቀርበው። በፓርቲው ውስጥ የተለመደ የቅሬታ አቀራረብ እያለ ጉዳዩን ወደ ጋዜጣ ይዞ መውጣት ለምን አስፈለጋቸው? ቅሬታ ያለው አካል ቅሬታውን ለኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን ለምን አላቀረበም?

ዲሲፕሊን ኮሚቴው ውሳኔውን የሰጠሁት ኮረም ሞልቶ ባደረግነው ውይይት መነሻ ነው የሚል ምላሽ አቅርቧል። የኮሚቴው ውሳኔ ምንም ይሁን ምንም ቅሬታ ያለው ወገን ለኮሚሽኑ ይዞ መቅረብ ነበረበት እንጂ፣ በጋዜጣ ላይ ጉዳዩን ይዞ ብቅ ማለቱ በራሱ የዲሲፕሊን ግድፈት ተደርጎ የሚወሰድ ነው። በነገራችን ላይ አይደለም በዲሲፕሊን ኮሚቴ ውሳኔ ላይ በኮሚሽኑ ውሳኔን አሰጣጥ ላይ ቅሬታ አለኝ የሚል አካል ካለ ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍርድ ቤቶች አቅርቦ መዳኘት የሚችልበት አሰራር በፓርቲያችን ውስጥ አለ። ስለዚህም በእኛ አረዳድ ጉዳዩን በሕግ አግባብ ሳይኬድበት ለጋዜጣ ማቅረብ የተፈለገው ከቀናነት የመነጨ ሳይሆን፣ በማር የተለወሰ መርዝ አድርገን ነው የምንወስደው።

ሰንደቅ፡- በነገራችን ላይ በዚህ ጋዜጣ ከመስተናገዱ በፊት፣ በፓርቲያችሁ ልሳን ጉዳዩ መስተናገዱንስ እንዴት ያዩታል?

አቶ አበራ፡- በፓርቲያችን ልሳን ላይ የወጣበት እና በሌሎች ጋዜጦች ላይ የወጣበት ጊዜ በጣም ተቀራራቢ ነው። እያልን ያለነው በፓርቲያችን ልሳንም ሆነ በግል ጋዜጦች የተስተናገደበት ሁኔታ ሕግን የተከተለ አይደለም። ቁምነገሩ የአሰራር ጥያቄ እንጂ ጉዳዩ የተስተናገደበት መገናኛ ብዙሃን አይደለም። በሁለቱም መስተናገዱ ስህተት ነው።

ሌላው ከተሰጠው ሥልጣን ውጪ የዲሲፕሊን ኮሚቴውን ውሳኔ አልቀበልም በማለት ሥራአስፈፃሚው በፓርቲው ልሳንና በሌሎች መገናኛዎች የተዘገበው ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ኮሚሽኑ መግለጫ አውጥቷል። ለባለድርሻ አካላትም እንዲደርስም ይህ መግለጫ ተበትኗል። ፓርቲውም በሕግ እንጂ በተወሰኑ ሰዎች ፍላጎት እንደማይመራ መታወቅ አለበት።

ሰንደቅ፡- የአንድ ፖለቲካ ፓርቲ ከፍተኛው አስፈፃሚ አካል፣ ሥራአስፈፃሚው መሆኑ ይታወቃል። ይህ አካል ስራዎቹን በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ያከናውናል ተብሎ ይገመታል። ከዚህ አንፃር እርስዎም ከላይ እንዳሰፈሩት፣ ሥራአስፈፃሚ ከስልጣኑ በላይ በመሄድ የዲሲፕሊን ኮሚቴውን ውሳኔ አልቀበልም ያለበት ፍላጎት ምንድን ነው ብላችሁ ትወስዳላችሁ?

አቶ አበራ፡- ፍላጎታቸው የሚመስለኝ በቀጣይ በሌሎች አመራሮች ላይ የሚታዩ ክሶች አሉ። እነዚህ ክሶች ከመቅረባቸው በፊት በሕግ አሰራሩ ላይ አላስፈላጊ ጫናዎች ለማሳደር ነው። ይህም ሲባል ዲሲፕሊን ኮሚቴው በአራት የፓርቲው አባላት ላይ የወሰደው እርምጃ ይህንን ከመሰለ፣ ነገስ ምን ሊወሰድ ይችላል የሚል ድንጋጤ ክስ በሚጠብቃቸው አመራሮች ላይ ውሳኔው፣ ድንጋጤ ፈጥሯል። የትኛውንም ያህል ጫና ለመፍጠር ቢፈለጉም፣ ከሕግ በላይ መሆን የሚችል ግለሰብም ሆነ አካል በፓርቲያችን ውስጥ ሊፈጠር እንደማይችል ከወዲሁ ግንዛቤ መወሰድ አለበት።

ሰንደቅ፡- የዲሲፕሊን ኮሚቴው ውሳኔ ኮረም ባልሞላበት የተወሰነ ነው እየተባለ ነው። ይህ ከሆነ እውነቱ አላስፈላጊ ግፊት መፍጠር ተደርጎ ሊወሰድ እንዴት ይችላል?

አቶ አበራ፡- አለመታደል ሆኖ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሴራ ፖለቲካ ነው። በመከራከሪያት የቀረበው ኮረም አልሞላም አንድ ሰውም አልፈረመም የሚል ነው። በመተዳደሪያ ደንባችን መሰረት ከሰባት የዲሲፕሊን ኮሚቴዎች፣ አራትና ከዚያ በላይ ከተገኙ ኮረም ሞልቷል ሲል ይደነግጋል። በዚህ መሰረት የዲስፕሊን ኮሚቴው ጉዳዩን ለመመልከት ስብሰባ ሲቀመጡ አራት አባላት በመገኘታቸው፣ ስብሰባው ኮረም ሞልቶ መጀመሩን ያረጋግጣል።

በስብሰባ አሰራር ቃለ ጉባኤ የሚፈረመው፣ በቀጣይ ስብሰባ ላይ ተነቦ የነበሩ አባላት ካደመጡና ከተስማሙ በኋላ ነው። በቃለ ጉባኤው ላይ የልዩነት ሃሳብ ያለው ሰው፣ ስሙ ተጠቅሶ በቃለ ጉባኤው ላይ የልዩነት ሃሳቡ ይሰፍርለታል። በቃለ ጉባኤው ላይ የውሳኔ ሃሳብ የሚሰጥበት ከሆነ በስብሰባው ላይ የተካፈሉ አባላት ድምጽ ይሰጣሉ። በአብላጫ ድምጽ ውሳኔ በጉዳዩ ላይ ያርፋል። ስለዚሀም ኮረም ሞልቶ ስብሰባ ከተጀመረ ውሳኔ የሚሰጠው በነበሩ አባላት ብቻ መሆኑ መታወቅ አለበት። ለምሳሌ የዲስፕሊን ኮሚቴው ስብሰባውን ሲጀምር በአራት የኮሚቴ አባሎች በመሆኑ፣ ስብሰባው የተከፈተው በመተዳደሪያው ደንብ መሰረት ኮረም ሞልቶ መሆኑን ለመረዳት ይቻላል። በውሳኔ አሰጣጡም ላይ የተገኙት አራት አባላት ብቻ ናቸው ድምጽ መስጠት የሚችሉት። ከዚህ መነሻ ነው፣ አንዱ የዲሲፕሊን ኮሚቴ እኔ ባልፈረምኩት ሁኔታ ውሳኔ ተላልፏል በሚል የፓርቲው የውስጥ አሰራር ለአደባባይ የበቃው። የፖለቲካ ሴራውና ጠለፋውም እዚህ ላይ ነው የሚጀምረው። ቅሬታ ያቀረበው የኮሚቴው አባል በተቃውሞ እንኳን ድምጽ ቢያዝለት፣ አሁን የተሰጠው የውሳኔ ሃሳብ ሶስት ለአንድ በሆነ ድምጽ ያልፋል። ይህ እውነት ጠፍቷቸው አይደለም ወደ ጋዜጣ የሄዱት፣ የነገን ተከሳሽነት በአላስፈላጊ ጫናዎች ለማምለጥ ከመፈለግ እንጂ።

ሰንደቅ፡- የዲስፕሊን ኮሚቴው በተገቢው መንገድ ኃላፊነቱን ተወጥቷል እያሉኝ ነው?

አቶ አበራ፡- ላስረዳህ የሞከርኩት የፓርቲው የውስጥ አሰራር ከሕግ አግባብ ውጪ ለአደባባይ እንዲወጣ እንዴት እንዳደረጉት ነው። ከዚህ ውጪ የዲሲፕሊን ኮሚቴው የሰጠው ውሳኔ የመጨረሻ ውሳኔ አይደለም። በውሳኔው ላይ ቅሬታ ያለው ወገን ካለ በሚያቀርበው የይግባኝ ቅሬታ መሠረት የኦዲትና የምርመራ ኮሚሽኑ የሚመለከተው ይሆናል። ይግባኝ ባልቀረበበት ሁኔታ ግን ኮሚሽኑ ጉዳዩን ለማየት ምንም አይነት የህግ ድጋፍ አይኖረውም። በመተዳደሪያው ደንብ መሠረት በአስራ አምሰት ቀናት ውስጥ ይግባኝ ካላሉ ውሳኔው የጸና ይሆናል። በተለየ ሁኔታ እያየን ያለነው የአቶ ዮናታን ተስፋዬ ጉዳይ ነው።

ሰንደቅ፡- እስካሁን የተነጋገርነው ከአሰራር አንፃር ነው። ሥራአስፈፃሚው ሆነ እርምጃ የተወሰደባቸው አባላት በክሱ ይዘት ላይም ተቃውሟቸውን በይፋ ነው ያቀረቡት። ይህም ሲባል የክሱ ይዘት የግለሰቦችን የመናገር የመጻፍ መብቶችን የተጋፋ ነው ሲሉ ከሰዋል። በዚህ ላይ ኮሚሽኑ ምን አስተያየት አለው?

አቶ አበራ፡- አንድ ሰው የፓርቲ አባል የሚሆነው ከራሱ የተወሰነ ነፃነቱን ቀንሶ ነው። ይህም ሲባል ለፓርቲ ፕሮግራም እና ደንብ እገዛለሁ የሚል የውል ስምምነት ውስጥ ስለሚገባ ነው። ስለዚህም የአንድ የፓርቲ አባል አስተሳሰቡም ሆነ አፃፃፉ ከፓርቲው ደንብ እና ፕሮግራም ጋር አንድ የሆነ የሚመጋገብ መሆን አለበት። ከዚህ ውጪ በራስ ፍላጎት መነሻ የሚፈጸሙ ማናቸውም አይነት ተግባራት በዲስፕሊን ኮሚቴ የሚታዩ ነው የሚሆኑት።

የፓርቲውን የማዕዘን ድንጋይ የሆኑ የግለሰቦችን ነፃነቶች ወደ ቡድን መብት በመውሰድ አደባባይ ላይ አውጥቶ ለክርክር ማብቃት በፓርቲው ደንብ ያስቀጣል። በፓርቲው ውስጥ በዘር በሃይማኖት በቋንቋ እና በተለያዩ መንገዶች ከፋፋይ የሆኑ ነገሮች የሚሰራ በሕግ እንደሚቀጣ የፓርቲው ደንብ ይደነግጋል። ስለዚህም የፓርቲውን ደንብ አልፎ ስለአንድ ማሕበረሰብ በብሔር ወይም በሌላ መልኩ ለመከራከር አትችልም። አንዱን ማሞገስ ሌላውን ማንኳሰስ በግለሰቦች ነፃነት ስም የሚታለፍ ተግባር አይደለም። ፓርቲው በዜጎች ትስስር እንጂ በቡድን ፍረጃ ላይ የቆመ አይደለም።

ሌላው ይህ የክስ ይዘት ትክክለኛነት መነሳት ያለበት ክሱ ከመታየቱ በፊት ነበር። ክሱ መደመጥ ከጀመረ እና ውሳኔ በተወሰነ ደረጃ ከተሰጠው በኋላ፣ አሁን ላይ ስለክሱ ይዘት ማውራት ተገቢ አይደለም። ተቀባይነትም የለውም። ለዚህም ነው አካሄዳቸው ቀናነት የጎደለው ነው የምንለው። በጋዜጣ ላይ ያቀረቡትን የመከራከሪያ ነጥቦች በፓርቲው ደንብ ስርዓት መከራከር የተከለከሉ ይመስል በዚህ መሰል ተግባር መሰማራታቸው ኃላፊነት የጎደለው ስራ ነው።

ሰንደቅ፡- የኦዲትና የምርመራ ኮሚሽኑ ድምጽ የተሰማ ዛሬ ነው። በፓርቲያችሁ ዙሪያ የገንዘብ ምዝበራዎች እንዳሉ በተደጋጋሚ በመገናኛ ብዙሃን ሲገለጽ ነበር። ካለባችሁ ኃላፊነት አንፃር ይህን ጉዳይ እንዴት ነው የምትመለከቱት?

አቶ አበራ፡- ምርመራ የተጀመረባቸው ፋይሎች አሉ። ምርመራ ባልተጠናቀባቸው ፋይሎች ላይ ደግሞ ምንም አስተያየት መስጠት አልችልም። የምርመራው ውጤት ነው የሚወስነው። ይህ ባልታወቀበት ሁኔታ ምዝበራ አለ ወይም የለም ለማለት አደጋች ነው። አጣርተን ስንጨርስ የደረስንበትን የማጣራት ውጤት ይፋ እናደርጋለን።

ሰንደቅ፡- የኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን በይግባይ አይቶ ውሳኔ የሰጣውቸው ፋይሎች አሉ?

አቶ አበራ፡- ከዚህ በፊት አሁን የዲሲፕሊን ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆነችው በሥራአስፈፃሚው ከፓርቲ ከኃላፊነቷ እንድትነሳ ተደርጋ ነበር። ቅሬታዋን ለኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን አቅርባ በይግባኝ ጉዳዩ ሲታይ ነበር። በምርመራ በተደረሰው ውሳኔ መሰረት ከሕግ አግባብ ውጪ መነሳቷ ተደርሶበት ወደ ኃላፊነቷ እንድትመለስ ተደርጓል። ሌላው የአባል ፎርም ሳይሞሉ ውሳኔ በተላለፈባቸው ሰዎች የተሰጠውን ውሳኔ ተገቢ ባለመሆኑ ፋይሉ እንዲዘጋና ክሱ ውድቅ እንዲሆን የተወሰነበት ሁኔታም አለ። በአጠቃላይ ከከፍተኛ አመራር እስከ ተራ አባላት ድረስ ውሳኔ ሰጥተን ቀጥተናል። ለጠቅላላ ጉባኤውም ሪፖርት አቅርበናል። ሌሎችም አሉ።

ሰንደቅ፡- አቶ ዮናታን ተስፋዬ በማረሚያ ቤት እያሉ ጉዳያቸውን መመልከት ተገቢ ተደርጎ የሚወሰድ ነው? በዚህ ላይ ኮሚሽኑ ምን ይላል?

አቶ አበራ፡- ባሰራጨነው መግለጫ ላይ በግልፅ እንዳሰፈርነው የአቶ ዮናታን ተስፋዬን ጉዳይ እየመረመርነው ይገኛል። ከምርመራው በኋላ ውሳኔ ያገኛል። ሆኖም ግን በዚህ ጋዜጣ ላይ አቶ ዮናስ በመከራከሪያት የአቶ የሸዋስ ጉዳይ አንስተው ያቀረቡት ፈጽሞ ሃሰት መሆኑ መታወቅ አለበት። አቶ የሽዋስ በማረሚያቤት እያሉ በሕግ የሚያስጠይቅ ክስም አልቀረበባቸውም። ይህ ባልሆነበት ሁኔታ የምክር ቤት ሰብሳቢውን አቶ ይድነቃቸውን ለመወንጀል መፈለጋቸው ኃላፊነት የጎደለው ተግባር መሆኑ ግንዛቤ መወሰድ አለበት። ውንጀላውንም ያቀረቡት ግለሰብ እውነትን በዚህ ደረጃ ለማዛባት ለምን እንደፈለጉ ለማንም የማይገባ አቀራረብ ነው።

ሰንደቅ፡- አሁን ካለው አጠቃላይ ሁኔታው ፓርቲው ሕጋዊ እና ሕገወጥ መስመሮችን በሚያጣቅሱ አመራሮች መካከል ላይ ይገኛል ማለት ይቻል ይሆን?

አቶ አበራ፡- ይህንን የሚወስነው በያዝናቸው ፋይሎች ላይ ምርመራዎችን ካጠናቀቅን በኋላ በሚገኘው ውጤት ነው። በርግጥ ሥራአስፈፃሚው መግለጫ እሰጣለሁ እያለ የተሰጠ ውሳኔን እስከመሻር የሄደበት ሁኔታ ነው ያለው። እነዚህ እና ሌሎች ጉዳዮችን ጠቅላላው ጉባኤ እንዲመለከታቸው ስራዎች እየተሰሩ ነው የሚገኙት። ከዚህ በፊትም ፓርቲው በርካታ ችግሮችን ያለፈ በመሆኑ አሁንም የተፈጠረውን ችግሮች በብቃት በጠቅላላው ጉባኤ ውሳኔ እንደምንፈታው እርግጠኞች ነን።

The post “ለጋዜጣ ጉዳዩን ማቅረብ የተፈለገው ከቀናነት በመነጨ ሳይሆን፤ በማር የተለወሰ መርዝ ነው” – አቶ አበራ ገብሩ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live