Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

Hiber Radio: በኢትዮጵያ ሰራዊቱ በኦሮሚያ የተቀሰቀሰውን ትግል የሚቀላቀልበት ጊዜ ሲመጣ ትግሉን ይቀላቀላል ሲል ጃዋር መሐመድ ገለጸ፣የአውሮፓ ሕብረት ፓርላማ በ ያሳለፈው ጠንካራ ውሳኔ በተግባር እንዲውል ኦነግ ጠየቀ፣የአውሮፓ ፓርላማ ውሳኔ የአገር ቤቱ ትግል ውጤት መሆኑ ተገለጸ፣ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ባለቤት የእንግሊዝ መንግስት ክህደት መፈጸሙን ገለጹ፣ በኢትዮጵያ እየታየው ያለው ያለመረጋጋት እና የደህንነት እጦት ምዕራባዊያን ኢንቨስተሮችን እንዳያሸሽ አስግቷል የሚሉና ቃለ መጠይቅ ከጃዋር መሀመድ ጋር፣የአቶ ነአምን ዘለቀ ስለሰራዊቱ የተናገሩትና ሌሎችም አሉን

0
0
Hiber
የህብር ሬዲዮ ጥር 15 ቀን 2008 ፕሮግራም

<…የአውሮፓ ፓርላማ ውሳኔ ሕግ ነው አገራቱ ተግባራዊ የሚያደርጉት ትልቅና ጠንካራ ውሳኔ ነው።ይሄበኦሮሞ ትግል ውጤት የተገኘ እንጂ አውሮፓውያኑ ዝም ብሎ ስለፈለጉ ብቻ የሆነ አይደለም። ሌላውምበኦሮሞ እንደታየው በመግለጫ ብቻ ሳይሆን በተግባር ስራ መስራት አለበት።ተቃውሞን በመግለጫ ብቻጥቅም የለውምሰራዊቱም የተነሳውን ተቃውሞ እንደ  ሀኪሙ፣መምህሩ፣ሰራተኛው ሁሉ ጊዜው ሲደርስይቀላቀላል። ሰራዊቱ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ አመራሩም ተቃውሞውን ይቀላቀለቀል አስቀድሞ ታስቦበትየተሰራበት ስትራቴጂ ነው ።ጊዜው ሲደርስ ሁሉም ይታያል…>   ጃዋር መሐመድ የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክዋና ዳይሬክተር የአውሮፓ ፓርላማን ውሳኔ መሰረት አድርገን በወቅታዊ ጉዳይ ለጠየቅነው    ከሰጠን ቃለመጠይቅ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)

የአርበኞች ግንቦት ሰባት የኦርላንዶ ፍሎሪዳ የገቢ ማሰባሰቢያ በተመለከተ (ቆይታ ከዝግጅቱ አስተባባሪዎችጋር)

<<…ሰራዊቱ ብሄራዊ መነሳሳት ሲኖር ሁሉንም ወገን የሚያሳትፍ አጀንዳ ተቀርጾ ሕዝባዊ እምቢተኝነቱምሆነ የትጥቅ ትግሉ ተጠናክሮ ሲቀጥል ከሕዝቡ ጎን ይሰለፋ።በጭቆና ውስጥ ያለ በዘረኛና ባልተማሩትየወያኔ  የጦር ጄኔራሎች የሚመራ ሰራዊት እነሱ እንዳሰቡት አብሯቸው በአንድ ላይ የሚቆም አይደለም።ዛሬ በኦሮሞ አካባቢ የሚደረገው ትግል በሁሉም አካባቢዎች ሕዝቡ ለመብቱ እምቢ ለወያኔ አልገዛም ብሎመንቀሳቀስ አለበት። ለዚህም ንቅናቄያችን…> አቶ ነአምን ዘለቀ የአርበኞች ግንቦት ሰባት የውጭ ግንኙነትሀላፊ በኦርላንዶ ፍሎሪዳ ተገኝተው ካደረጉት ንግግር መካከል ሰራዊቱን በተመለከተ ከተናገሩትየተወሰደ(ቀሪውን ያዳምጡት)

 

በቬጋስ የሚገኘው የታክሲ ተቆጣጣሪ ባለስልጣን እንዲፈርስ የተጠየቀበትን የኦዲት ሪፖርት መሰረት አድርጎየተደረገ ውይይት (ቀሪውን ያዳምጡት)

 

በቱኒዚያ ውስጥ ሰሞኑን የአንድ ስራ አጥ ወጣት ራሱን በኤሌክትሪክ ሽቦ ላይ ተንጠልጥሎ መሞትን ተከትሎያገረሸው አመጽ እና ያስከተለው ፖለቲካዊና ማህበራዊ ቀውስ  (ልዩ ዘገባ)

 ሌሎችም

ዜናዎቻችን

በኢትዮጵያ ሰራዊቱ በኦሮሚያ የተቀሰቀሰውን ትግል የሚቀላቀልበት ጊዜ ሲመጣ ትግሉን ይቀላቀላል  ሲልጃዋር መሐመድ ገለጸ

የአውሮፓ ፓርላማ ውሳኔ የአገር ቤቱ ጠንካራ ትግል ውጤት መሆኑ ተገለጸ

የአውሮፓ ሕብረት ፓርላማ በኢትዮጵያው አገዛዝ ላይ ያሳለፈው ጠንካራ ውሳኔ በተግባር እንዲውል ኦነግጠየቀ

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ባለቤት የእንግሊዝ መንግስት ክህደት መፈጸሙን ገለጹ

በኢትዮጵያ እየታየው  ያለው ያለመረጋጋት እና  የደህንነት እጦት ምዕራባዊያን ኢንቨስተሮችን እንዳያሸሽአስግቷል

በአዋሳ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ

በኢትዮጵያ ውስጥ ለተንሰራፋው ድርቅ እና ርሃብ አለማቀፋዊ በቂ ማላሽ መታጣቱ የበጎ አድራጊድርጅቶችን  በእጅጉ ስጋት ውስጥ ከቷቸዋል

የነገረ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው በጠበቃና በቤተሰብ ሳይጎበኝ ሌላ ተጨማሪ ጊዜለፖሊስ ተፈቀደ

ግብጽ ኢትዮጵያዊያን ሰደተኖችን ከአገሯ አባረረች፣ታንዛኒያ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ሰደተኞችን ወደ እስርቤት መወረወሯ ታወቀ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

The post Hiber Radio: በኢትዮጵያ ሰራዊቱ በኦሮሚያ የተቀሰቀሰውን ትግል የሚቀላቀልበት ጊዜ ሲመጣ ትግሉን ይቀላቀላል ሲል ጃዋር መሐመድ ገለጸ፣የአውሮፓ ሕብረት ፓርላማ በ ያሳለፈው ጠንካራ ውሳኔ በተግባር እንዲውል ኦነግ ጠየቀ፣የአውሮፓ ፓርላማ ውሳኔ የአገር ቤቱ ትግል ውጤት መሆኑ ተገለጸ፣ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ባለቤት የእንግሊዝ መንግስት ክህደት መፈጸሙን ገለጹ፣ በኢትዮጵያ እየታየው ያለው ያለመረጋጋት እና የደህንነት እጦት ምዕራባዊያን ኢንቨስተሮችን እንዳያሸሽ አስግቷል የሚሉና ቃለ መጠይቅ ከጃዋር መሀመድ ጋር፣የአቶ ነአምን ዘለቀ ስለሰራዊቱ የተናገሩትና ሌሎችም አሉን appeared first on Zehabesha Amharic.


ከሰይፉ ፋንታሁን እና ሚኪያስ መሐመድ ቃለምልልስ በስተጀርባ – (ከሰራተኞቹ አንዱ)

Previous: Hiber Radio: በኢትዮጵያ ሰራዊቱ በኦሮሚያ የተቀሰቀሰውን ትግል የሚቀላቀልበት ጊዜ ሲመጣ ትግሉን ይቀላቀላል ሲል ጃዋር መሐመድ ገለጸ፣የአውሮፓ ሕብረት ፓርላማ በ ያሳለፈው ጠንካራ ውሳኔ በተግባር እንዲውል ኦነግ ጠየቀ፣የአውሮፓ ፓርላማ ውሳኔ የአገር ቤቱ ትግል ውጤት መሆኑ ተገለጸ፣ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ባለቤት የእንግሊዝ መንግስት ክህደት መፈጸሙን ገለጹ፣ በኢትዮጵያ እየታየው ያለው ያለመረጋጋት እና የደህንነት እጦት ምዕራባዊያን ኢንቨስተሮችን እንዳያሸሽ አስግቷል የሚሉና ቃለ መጠይቅ ከጃዋር መሀመድ ጋር፣የአቶ ነአምን ዘለቀ ስለሰራዊቱ የተናገሩትና ሌሎችም አሉን
0
0

Mikiyas
አርቲስት ሚኪያስ መሐመድ የተለያዩ ሰዎችን ‹‹ጎማ እናስመጣ›› እንዲሁም በአንድ ወቅት ንሮ የነበረውን የሲሚንቶ ገበያ ሰበብ በማድረግ ‹‹የማውቃቸው ሰዎች አሉና ሲሚንቶ አብረን እንነግድ›› በማለት ነበር እንቅስቃሴውን የጀመረው፡፡

ሚኪ ወደዚህ ስራ ሲገባ በቀላሉ የሚያውቃቸውንና ገንዘብ አላቸው ብሎ የሚተማመንባቸውን ሰዎች ማጥመድ ጀመረ፡፡ በዚህ ወጥመድ ውስጥ የተወሰኑ ባለሀብቶች ገብተውለት 8 ሚሊዮን ብር ገደማ ሲያገኝ የተጠቀሰውን ያህል መጠን ያለው ቼክም ፅፎ ሰጣቸው፡፡ ቼኩ በቂ ስንቅ(ገንዘብ) የሌለው መሆኑን ባለሀብቶቹ ሲረዱ እንደተጭበረበሩ የገባቸው ሲሆን፤ ከእነዚህ ሰዎች አንዱ(2 ሚሊዮን ብር የሰጡት) ጉዳያቸውን ይዘው ወደቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አቀኑ፡፡ የቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስም አቶ ሚኪያስ መሐመድን በጷግሜ ወር በቁጥጥር ስር አዋለው፡፡

በፖሊስ ጣቢያው ከሳሽና ተከሳሽ ፊት ለፊት ሲገናኙ ተከሳሽ ሚኪ ስቅስቅ ብሎ እያለቀሰ የከሳሽ እግር ስር ወድቆ ተማፀነ፡፡ ‹‹እንደራደር›› ሲልም ጥያቄ አቀረበ፡፡ በዚህ መሰረት ግማሽ ክፍያ ወዲያውኑ ለመስጠትና ቀሪውን ደግሞ በ15 ቀናት ውስጥ ለመክፈል ጊዜ እንዲሰጠው መደራደሪያ አመጣ፡፡ በዚህ መሐል ነው እንግዲህ ምስኪኑ ራስታ ዘፋኝ ህይወቱን ሙሉ ያጠራቀመውን ገንዘብ አንስቶ ለሚኪ የሰጠው፡፡ ሚኪም ከታደለ ሮባ የወሰደውን ገንዘብ ከተከሰሰበት 1.7 የሚሊዮን ብር ዕዳ ግማሹን ሊከፍል ቻለ፡፡

ይህ ሁሉ ሁኔታ ሲሆን ማለትም ሚኪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ሲውል ዛሬ እያስተባበለ ያለው ሰይፉ ፋንታሁን ሊያገባ ጥቂት ቀናት ቀርተውት ነበር፡፡ ሚዜውም ነበር፡፡ ሙሽራውና ሚዜዎች ስቲም ሊገቡ ቀጠሮ በነበራቸው ቀን ሚኪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ስለነበር ሳይገኝ ቀርቷል፡፡ ከእስር ከተፈታ በኋላ ሰርጉ ሲከናወን ይህንን ሚስጥር የሚያውቁት ሚኪና ታደለ ብቻ ነበሩ፡፡ እናም ውሾን ያነሳ… ተባባለው ተማማሉ፡፡

ከሰርጉ ስነስርዓት በኋላ የሚኪ ስልክ ድንገት ዝግ መሆኑ ግን ግራ የሚያጋባ ሆነ፡፡ በዚያ ላይ አሜሪካ የመግባቱ ጉዳይም መወራት ጀመረ፡፡ እሱ ግን በቫይበር ከሚደወሉለት ስልኮች ውስጥ የአንድ ሰውን ጥሪ ብቻ ያነሳ ነበር፡፡ የሰራዊት ፍቅሬን!!

በዚህ ወቅት ከሚኪያስ መሐመድ ቼክ የተሰጣቸው ሰዎች በሙሉ ወደባንክ መጉረፍ ጀመሩ፡፡ ቼኩን አስመትተውም አርቲስቱ የሚመጣበትን ቀን መጠባበቅና መፀለይ ሆነ ስራቸው፡፡ ይሁንና በመሀል ሽምግልና ተብሎ እነዚህ ቼኮች በሙሉ ተሰበሰቡ፡፡

(በዚህ ወቅት አማን(ጀርመኑ) ለተባለ ወጣት ከሚኪ የተፃፈለትን የ350ሺህ ብር ቼክ ልብ ያለው ሰው አልነበረም፡፡ ይህ ወጣትም ቼኩን አስመትቶ ጉዳዩን አቃቤ ህግ ጋር አድርሶታል፡፡)

Mikiyas Mohamed

ከሽምግልናው ጎን ለጎን ድምፃዊ ታደለ ሮባ ‹‹ይህን ያህል አመት የሰራሁበትን ገንዘብ ዘረፈኝ፤ ጉድ አደረገኝ›› እያለ የሚኪ እናት ቤት ይመላለስ ነበር፡፡ እናትየውም ‹‹አይዞህ ቤቴን ሸጬም ቢሆን እከፍላችኋለሁ እንጂ ልጄን ከሳችሁ አታሳስሩብኝ›› ይሉ ጀመር፡፡

የእናትየው ሀዘንና ቼክ የተጭበረበሩ ሰዎች ለቅሶ ያሳዘነው ዮናስ ቬጋስ ‹ጉዳዩን ለኔ ተውት›› ብሎ እንቅስቃሴ ጀመረ፡፡ እንቅስቃሴው ሚኪን ከአሜሪካ አስመጥቶ የእናቱን ቤት ሸጦም ቢሆን ቼክ ለተሰጣቸው ሰዎች ገንዘባቸው እንዲመለስላቸው የማድረግ ነው፡፡

በመሆኑም ዮናስ ቬጋስ ወደአሜሪካ አቀናና ከሚኪ ጋር ተገናኘ፡፡ ከቀናት በኋላም ታደለ ሮባ ተከተለው፡፡

የሚገርመው ‹‹በህይወት ዘመኑ የሰራበትን ገንዘብ የበላው›› እና ስልኩን ዘግቶ የጠፋበት ሚኪያስ መሐመድ በአሜሪካ ታደለ ሮባን አየር ማረፊያ ድረስ ሄዶ በመቀበል ሰርፕራይዝ አድርጎታል፡፡

በቀጣይነት ድርድሮችና ውይይቶች መደረግ ጀመሩ፡፡ በአደራና በሽምግልና ቼኮቹ የተቀመጡት ሰራዊት ፍቅሬ ጋር በመሆኑ ሚኪ በቀጥታ ለሰራዊት በመደወል ሁኔታውን አረጋገጠ፡፡ ከዚህ በኋላ ወደኢትዮጵያ ተመልሶ አጭበርብሮበታል የተባለባቸውን ቼኮች ለመክፈል ተስማማ፡፡ የሚመለስበት ቀንም ተቆረጠ፡፡ ነገር ግን በዚህ መሀል አንድ ችግር ተፈጠረ፡፡ 350 ሺህ ብር የተበላው ወጣቱ አማን(ጀርመኑ) ‹‹ክሴን አላነሳም፤ በክሱ እቀጥልበታለሁ›› ሲል በአቋሙ ጸና፡፡ ሚኪያስም ‹‹እንደዚህ ከሆነማ አልመለስም በቃ!!›› ሲል ሀሳቡን የመቀየር ነገር አመጣ፡፡ አማንን(ጀርመኑን) የሚያውቁት ሰዎች በሙሉ ክሱን እንዲያቋርጥ ቢወተውቱትም አማን ግን በእንቢታው ፀና፡፡ (ይህኛውን ታሪክ በቀጣይ እንመለስበታለን)

የአማን ነገር እንደማይሆን ሲታወቅ ‹‹ያበጠው ይፈንዳ›› በሚል ይመስላል ሚኪያስ መሀመድና ታደለ ሮባ ከሎስ አንጀለስ በአንድ አውሮፕላን ተሳፍረው ቅዳሜ ጠዋት አዲስ አበባ ገቡ፡፡

አዲስ አበባ ከገቡ በኋላ ሚኪያስ መሀመድ ለሽማግሌዎቹ አንድ ተማፅኖ አቅርቧል፡፡ ይህም ገንዘብ እንዳላጭበረበረና አሜሪካ የሄደው ለመዝናናት እንደሆነ በሚዲያዎች የሀሰት ዘገባ እንዲሰራለት ነው፡፡ ይህን የሀሰት ዘገባ ሰይፉ ፋንታሁን ብቻ ‹‹እሺ›› ብሎ ሲቀበል ሌሎች ለሙያቸው ያደሩ ጋዜጠኞች አንሰራም ብለዋል፡፡

እናም ዘሃበሻ ቀደም ብላ እንደጠቀሰችውም ሚኪያስ መሀመድ ቅዳሜ ምሽት ሰይፉ ሬዲዮ ላይ ቀርቦ የውሸት መአቱን የደረደረው ለዚህ ነው፡፡ እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ጉዳዩን እያወቅን ዝም ብለን የቆየነውን እኛን ሰራተኞቹን መወንጀል ለምን አስፈለገው? እንላለን፡፡

The post ከሰይፉ ፋንታሁን እና ሚኪያስ መሐመድ ቃለምልልስ በስተጀርባ – (ከሰራተኞቹ አንዱ) appeared first on Zehabesha Amharic.

ዛሬ በሐዋሳ ለ6ኛ ግዜ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ | #ለሐዋሳ እንጸልይ!

0
0

Awasa Ketema

(ዘ-ሐበሻ) ዘ-ሐበሻ ትናንት እሁድ በዘገበችው መሰረት ለ3 ጊዜያት የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር:: ዛሬ ከአዋሳ አካባቢ ያነጋገርናቸው ወገኖች እንደገለጹልን ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ በ24 ሰዓታት ውስጥ ለ6ኛ ጊዜ የመሬት መንቀጥቀጡ ተከስቷል::

ይህ ዜና ከተጠናከረበት 20 ደቂቃ በፊት ለ6ኛ ጊዜ የመሬት መንቀጥቀጡን ያስታወቁት ዘ-ሐበሻ ያነጋገረቻቸው ወገኖች በደረሰው አደጋ በርካታ ወገኖች ወደ ሆስፒታል እንደተወሰዱ… በፎቅ ላይ የሚኖሩ ወገኖችም ወደ ምድር መወረዳቸውን ነግረውናል::

በሐዋሳ ነዋሪው በከፍተኛ ሁኔታ ተደናግጦ ይገኛል::

ለሐዋሳ እንጸልይ!

The post ዛሬ በሐዋሳ ለ6ኛ ግዜ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ | #ለሐዋሳ እንጸልይ! appeared first on Zehabesha Amharic.

የኢትዮጵያ ሙስሊም ፈተና በ224 ደቂቃዎች (በዘላለም ክብረት)

0
0

በዘላለም ክብረት
ክፍሉ ከኮሪደሩ ላይ ከተንጠለጠለ አምፖል በሚመጣ ብርሃን ፈገግ ብሏል፡፡ እኔም ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ወደክፍሉ ስገባ ከክፍሉ አንደኛው ጫፍ ላይ አንድ ቀጠን ያለ ሰው ድምፁን በትንሹ ከፍ አድርጎ ቁርዓን ‹እየቀራ› ነበር፡፡በክፍሉ ሌላኛው ጫፍ ላይ ደግሞ አንድ ፍራሽ፣ አንድ የውሃ ጀሪካን እና ትንሽ ልብሶች በፌስታል ውስጥተቀምጠዋል፡፡ በሌላኛው የክፍሉ ጫፍ ደግሞ የሽንት ባልዲ – ሽታውን ለመቀነስ ሲባል በግማሽ ውሃ ተሞልቶተቀምጧል፡፡ ክፍሉ ውስጥ እንደገባሁ አንዱ ጫፍ ላይ ትንሽ ቆም ካልኩ በኋላ በክፍሉ ውስጥ ያገኝሁት ብቸኛውሰው ፍራሹ ላይ እንድቀመጥ በእጁ ሲጠቁመኝ ቁጭ አልኩ፡፡ ፍራሽ ላይ እንደተቀመጥኩ በፍራሹ ጫፍ ላይ የጆንግሪሻም ‘The Last Juror’ መፅሃፍ ተቀምጦ አየሁት፤ አንስቼ ስመለከተው ክፍሉ ውስጥ ያገኘሁት ሰው ቁርዓንመቅራቱን ጨርሶ እንግሊዝኛ እችል እንደሆነ ጠይቆኝ ማውራት ጀመረ፡፡ ስሙ ሐሰን ጃርሶ እንደሚባል ነግሮኝ፤በመፅሃፍ እጥረት ምክንያት ይሄን መፅሃፍ ለአምስተኛ ጊዜ እያነበበው እንደሆነም አጫወተኝ፡፡ መፅሃፉን ቃሊቲ እስርቤት በታሰረበት ወቅት እስክንድር ነጋ እንደሰጠውም ነገረኝ፡፡ እኔም ለምን እንደታሰርኩ እንደማላውቅ ነግሬው እሱለምን እንደታሰረ ስጠይቀው በዜግነቱ ኬኒያዊ፣ የቀድሞ የዓልሸባብ ወታደር እንደነበርና አሁን የ17 ዓመት ፍርደኛ ሆኖከቃሊቲ የከፍተኛ ጥበቃ እስር ቤት ከጥቂት ሰዓታት በፊት ተዘዋውሮ እንደመጣ ነገረኝ፡፡ ይህ ሚያዚያ 17/2006 የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ዘርፍ (ማዕከላዊ) በገባሁበት ወቅት የገጠመኝ ጉዳይ ነው፡፡
ስለ ሐሰን ጃርሶ ከመታሰሬ በፊት አንድ ሰሞን ከአዲስ ዘመን እስከ ኢቴቪ የተቀባበሉት ጉዳይ ነበርና ሁኔታዎቹን ሲተርክልኝ ትንሽ ነገር በጊዜው ማስታወስ ችዬ ነበር፡፡

የሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እና ተባብራችኋል ተብለው የተፈረደባቸው ኢትዮጵያዊያን © ማሕበራዊ ሚዲያ

የሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እና ተባብራችኋል ተብለው የተፈረደባቸው ኢትዮጵያዊያን © ማሕበራዊ ሚዲያ


የቀድሞው ኢቴቪ የአሁኑ ኢቢሲ ‹እስልምና› እና ‹ሽብርተኝነትን› አስመልክቶ በተለይም በአለፉት አራት ዓመታት የተለያዩ ‹ዘጋቢ ፊልሞችን (documentaries)› ያቀረበ ሲሆን፤ እኔም ለአጭር ጊዜ በታሰርኩበት ወቅት ‹በዘጋቢ ፊልሞቹ› ውስጥ የተጠቀሱትን ግለሰቦችና ቡድኖች የማግኘትና በጉዳዩ ላይ የመነጋገር ዕድል አጋጥሞኝ ስለነበር ይሄን አጋጣሚ በብሔራዊ ቴሌቪዥኑ ‹እስልምና› እና ‹ሽብርተኝነትን› አስመልክቶ ከቀረቡ አምስት የተለያዩ ‹ዘጋቢ ፊልሞች› (አዲስ ግንባር፣ ጅሃዳዊ ሐረካት፣ ሐዘን ለመድረስ … ጉዞ ወደ ደሴ፣ የጥፋት መልዕክተኞች እና የማንቂያ ደወል) ጋር አያይዞ ማየት የዘጋቢ ፊልሞቹን ዓላማና የሙስሊሙን ፈተና ያሳየን ይሆናል በሚል ሐሳብ ነው ይሄን ፅሁፍ መፃፌ፡፡
ያለፉት አምስት ዓመታት በማሕበረሰብ ደረጃ ትልቅ ፈተና ከገጠማቸው ኢትዮያዊያን መካከል ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ጎልተው የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ፈተናው በዋነኛነት ከመንግስት በኩል የመጣ ሲሆን፤ ይሄን ተከትሎም የውስጥ ስነ መለኮታዊ እሰጥ አገባው ሙስሊሙን እጅግ ፈተና ውስጥ እንዲዘፈቅ አድርጎታል፡፡ በተለይም በታሕሳስ 2004 ገንፍሎ አደባባይ የወጣው የሙስሊሙ የመብት ጥያቄን ተከትሎ በተለያዩ አቅጣጫዎች ፈተናው የጨመረ ሲሆን መንግስት ጉዳዩ የመብት ጥያቄ ነው ብሎ ከመቀበል ይልቅ ‹የሽብርተኞች ስራ› ነው በማለት የመብቱን ጠያቂዎች የተለያዩ ስያሜዎች በመስጠት ጥያቄዎቹን አልቀበልም በማለት ቀጥሏል፡፡ ከዚህ እምቢተኝነት ጋር ተያይዞም መንግስት በተለያዩ ጊዜያት ተመሳሳይ ይዘት ያላቸውን ዘጋቢ ፊልሞች በብሔራዊ ቴሌቪዥኑ በማስተላለፍ የፕሮፓጋንዳ ቀዳሚነቱን ለመያዝ አሁን ድረስ እየደከመ ይገኛል፡፡ ፕሮፓጋንዳውን በዋነኛነት እየመራው የሚገኝው ደግሞ መንግታዊው ቴሌቪዥን ነው፡፡
መንግስታዊው ቴሌቪዥን ባለፉት አመስት ዓመታት ‹እስልምና› እና ‹ሽብርተኝነትን› አስመልክቶ ካቀረባቸው ዘጋቢ ፊልሞች መካከል ቀዳሚው በመግቢያዬ የጠቀስኩት ‹አዲስ ግንባር› የተባለው ዘጋቢ ፊልም ነው፡፡ የፊልሙ ዋነኛ ማጠንጠኛም አሸባሪው አል ሸባብ ኢትዮጵያ ውስጥ የራሱን ሕዋስ (cell) ለመዘርጋት ያደረገውን ጥረት የሚያሳይ ነው፡፡ ይሄን ድርጊት ተከትሎም ነው በጊዜው ጠ/ሚኒስትር የነበሩት መለስ ዜናዊ ‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የአልቃይዳ ሕዋስ ተገኝቷል፡፡ የዚህ ሴል አባላት ሁሉም ሰለፊ ናቸው›› በማለት ነበር ፓርላማ ቀርበው ንግግር ያደረጉት፡፡ የሕዋሱ አመራር እንደሆነ በዘጋቢ ፊልሙ የተገለፀው ኬኒያዊው ሐሰን ጃርሶ ለፍርድ ቤትም ሆነ እኔ ማዕከላዊ ባገኝሁት ወቅት እንደነገረኝ የዘጋቢ ፊልሙን ድምፀት (tone) ከመጠራጠር በቀር የአል ሸባብ አባል እንደሆነ እሱም አይክድም፡፡ ሐሰን እጅግ ብዙ ለመስማት የሚከብዱ ሁኔታዎችን እንዳለፈ የገለፀልኝ ሲሆን ኢትዮጵያ ውስጥ በቁጥር የሚበዛው ሙስሊም ነው ከሚል የራሱ እምነት ተነስቶ እዚህ መምጣቱን ገልፆልኛል፡፡ ከዚህ ባለፈ ሐሰንም ሆነ ድርጅቱ አል ሸባብ ስለ ኢትዮጵያ ብዙም የጠለቀ ግንዛቤ አላቸው ለማለት በማያስችል ሁኔታ መሬት ላይ ያሉ እውነታዎችን ለማየት ፍላጎቱ ያላቸው አልመሰለኝም፡፡
‹አዲስ ግንባርን› አሁን ከእስር ከተፈታሁ በኋላ ደግሜ ስመለከተው በቀጣይ ከመጡት ዘጋቢ ፊልሞች ጋር በማነፃፀር የዘጋቢ ፊልሙ ዋነኛው ማጠንጠኛ ሆኖ ያገኘሁት ወደ ስነ መለኮታዊው ጉዳይ ወርዶ ‹ሰለፊያ› ያለውን ቡድን ኢላማ አድርጎ መምታትን እና ነባሩ እስልምና ያለውን ‹ሱፊያ› አጉልቶ ማቅረብን ‹አል ሸባብ ሰለፊ ነው› በሚለው ገለፃው ውስጥ እናገኛለን፡፡ ብሎም ‹በዋህቢያ ወይም ሰለፊያ አስተምሮ እየተመሩ [ሊያጠፉን ነው] … እነዚህን ሰዎች ማጥፋት ነው፡፡ ከኢትዮጵያ እንዲጠፉ እንጠይቃለን እኛ› በማለት ብይን ይሰጣል፡፡
የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ጥያቄ አደባባይ የወጣበትን አንደኛ ዓመት በሚያከብርበት ጥር 2005 ደግሞ መንግስታዊው ቴሌቪዥን ብዙ ሰዎችን ያስቆጣውን እና ቴሌቪዥን ጣቢያውን በፍርድ ቤት እስከመቆም ያበቃውን ‹ጅሃዳዊ ሐረካት› ይዞ ብቅ አለ፡፡ በዚሕኛው ዘጋቢ ፊልሙ አማን አሰፋ በተባለ የአልሸባብ ወታደር የተመራን ‹ሐረካተይ ሸባብል ሙጃሂዲን ፊ ቢላድን ሒጅራቴይን› የተባለን አንድን ቡድን (እስከ አሁን ድረስ ጉዳዩ ገና የፍርድ ቤት ውሳኔ ያልተሰጠበት ቢሆንም ከሶስት ዓመታት በፊት በጊዜው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር የነበሩት ዶ/ር ሽፈራው ገ/ማርያም ‹ይህ ቡድን በኢትዮጵያ የተገኘው ሁለተኛው የአልቃይዳ ሕዋስ ነው› በማለት ፍርድ ሰጥተውበታል) የሙስሊሙን የመብት ጥያቄ ለመንግስት ለማቅረብ በሕዝብ የተወከሉትን የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ጋር (ገና ክስ በተመሰረተባቸው በሁለተኛ ወሩ) በማስተሳሰር የቀረበ ነው፡፡
ይሄን ዘጋቢ ፊልም አሁን በድጋሚ ስመለከተው እጅግ በጣም እያዘንኩ እና መጨረስ በተደጋጋሚ እያቃተኝ ነው፡፡ በእስር ላይ በነበርኩበት ወቅት በየእለቱ በዘጋቢ ፊልሙ ከቀረቡት ሰዎች ጋር እገናኝ ነበርና፡፡ አማን አሰፋ በተባለ የአልሸባብ ወታደር የተመራን ‹ሐረካተይ ሸባብል ሙጃሒዲን ፊ ቢላድን ሒጅራቴይን› የተባለውን ቡድን አስመልክቶ እኔ መናገር የምችለው በእስር ወቅት አግኝቻቸው ስለነበሩት ስለ አቶ አማን አሰፋ ብቻ ነው፡፡ አቶ አማን አሰፋ ለፍርድ ቤትም እንዳስረዱት እርሳቸውም ‹ሰልፉ እየተጎበኘ ነው› ባሉትና ዓቃቤ ሕግ በማስረጃነት ባቀረበባቸው መፅሃፋቸው እንደገለፁት የአልሸባብ ወታደር መሆናቸውን አልካዱም ነገር ግን በኢትዮጵያ ጥቅም ላይ አንዳችም ጉዳት ለማድረስ እንዳልተነሱ ገልፀዋል፡፡ የዚህ ቡድን አባላት ናቸው የተባሉ ሌሎች ግለሰቦችን አስመልክቶ ብዙም የማውቀው ነገር አለ ማለት ባልችልም፤ ክሳቸውን ተመልክቼ እንደ ጋዜጠኛ ሰለሞን ከበደ ያሉ ወጣቶች ምንም በማይገባቸው ጉዳይ በግፍ እንደታሰሩ አምናለሁ፡፡
ጅሃዳዊ ሐረካትን ስመለከት እጅግ ያሳዘነኝ ጉዳይ በሕይወታቸው ተያይተው የማይተዋወቁ ግለሰቦችን እና በፍፁም ለተለያየ አላማ የቆሙ ግለሰቦችን አንድ ላይ ‹ሁለቱ ቡድኖች፡ ከአልቃይዳ፣ ሻዕቢያ፣ አልሻባብና ግንቦት ሰባት ጋር የቀጥታ እና ተዘዋዋሪ ግንኙነት በመፍጠር … › በሚል ዘጋቢ ፊልሙ የፍርድ ውሳኔ ከመስጠቱ እጅግ በጣም አስቀድሞ ብይን ሰጥቶባቸዋል፡፡ የሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ (መአኮ) አባላት ከሆኑት እና አሁን በግፍ ተፈርዶባቸው በእስር ላይ ከሚገኙት አቡበክር አሕመድ፣ ካሚል ሸምሱ፣ አሕመድ ሙስጠፋ፣ ሼህ መከተ ሙሔ እና ያሲን ኑሩ (በመስከረም 2008 ከእስር የተፈታ)፤ እንዲሁም ከኮሚቴው ጋር ሰርታችኋል ተብለው የግፍ ሰለባ ከሆኑት በድሩ ሁሴን፣ ሙባረክ አደም እና አቡበክር አለሙ (በመስከረም 2008 ከእስር የተፈታ) ጋር በታሰርኩበት ወቅት እጅግ የቀረበ ግንኙነት ስለነበረኝ በዘጋቢ ፊልሙ ‹ሁለተኛው ቡድን› ተብሎ ስለተገለፀው ቡድን ብዙ መናገር እችላለሁ፡፡
የኮሚቴው አባላትም ሆኑ ከኮሚቴው ጋር ግንኙነት አላችሁ ተብለው የተከሰሱትን ግለሰቦች እጅግ የሚከበሩ እና አይነተኛ ዜጎች (ideal citizens) ሆነው ነው ያገኘኋቸው፡፡ የታሪክ፣ የፖለቲካ እንዲሁም የሐይማኖት ንፅፅራዊ (Comparative Religion) እውቀታቸው ከፍ ያለ፤ አይደለም ከሽብርተኝነት ጋር ከግለሰብ ፀብ ጋር እንኳን ስማቸው አብሮ መነሳት የሌለባቸው፤ ይሄ ሁሉ በደል ተፈፅሞባቸውና ስማቸው ጠልሽቶ እንኳን ቂም የሚባል ነገር ማንም ላይ የማይቋጥሩ ግለሰቦች ናቸው፡፡ ለሳይንሳዊ እውቀት ትልቅ ክብር የሚሰጡ (ከበድሩ ሁሴን ጋር ከስምንት ወራት በላይ አንድ ላይ አንድ ቤት ስንኖር በተደጋጋሚ አንስተን ያወራነው እና ሊያስረዳኝ የሚሞክረው ጉዳይ እሱ እጅግ ስለሚያደንቀው የታላቁ ስኮትላንዳዊ ፊዚስት ጀምስ ክለርክ ማክስዌል ‹Maxwell’s Equations› ነው፡፡ በድሩ ሀይማኖታዊ እውቀቱ ከፍ ያለ ከመሆኑ ባለፈ በእንደ ጋንዲ አይነት ሰዎች ታሪክ የሚመሰጥ፤ በእንደ ማክስዌል አይነቱ ፊዚስት የሚደመም ሰው ነው)፣ በየቀኑ የሚያነቡና የሚፅፉ (የኮሚቴው አባላት ከታሰሩ ወዲህ ከ20 በላይ መፅሃፍትን ከእስር ሆነው ማሳተማቸውን ማየቱ ብቻ ለዚህ በቂ ነው) እንዲሁም ለሌላ ሐይማኖት ተከታዮችም ሆነ ለእንደኔ አይነቱ ሐይማኖት አልባ (Atheist) ክብር የሚሰጡ ግለሰቦችም ናቸው፡፡ ይሄን ስፅፍ ብዙ ስሜታዊ የሚያደርጉ ነገሮች እየተፈታተኑኝ ነው፡፡
እንግዲህ መንግስታዊው ቴሌቪዥን ‹ጅሃዳዊ ሐረካት› በሚለው ዘጋቢ ፊልሙ ግፍ የሰራባቸው እነዚህን መልካም ሰዎች ነው፡፡ በእስር ላይ በነበርንበት ወቅት ስለ ‹ጅሃዳዊ ሐረካት› እያነሳን ብዙ ተሳስቀናል፡፡ አቡበክር አሕመድ በድብቅ ካሜራ የተቀረፀው በረመዳን የፆም ወቅት ያለማቋረጥ ከአስራ ሁለት ሰዓታት ለሚበልጥ ጊዜ ‹ምርመራ› እየተደረገበት እኩለ ሌሊት ላይ እንደሆነ እያነሳ ‹ሕዝብ እንደሆነ እውነቱን በማግስቱ አውቋል› እያለ የሚስቅ ሰው ነው፡፡
ለማንኛያውም ዘጋቢ ፊልሙ አሁንም ዋሃቢያ/ሰለፊያ ያለውን ቡድን የችግሮች ሁሉ መነሻ በማድረግ ነባሩ እስልምና ወይም ሱፊያውን በማወደስ ተጠንቀቁ ይለናል፡፡
ሶስተኛው በመንግስታዊ ቴሌቪዥኑ የቀረበው ዘጋቢ ፊልም ደግሞ በኢትዮጵያ ፈርስት ዶት ኮም ባለቤት አቶ ቢኒያም ከበደ የተዘጋጀው ‹ሀዘን ለመድረስ … ጉዞ ወደ ደሴ› የተባለው ዘጋቢ ፊልም ነው፡፡ ይህ ዘጋቢ ፊልም በዋናነት በደሴ ከተማ የተገደሉትን የሸህ ኑሩ ይማምን አሟሟት ለማሳየት የቀረበ ሲሆን፤ ሸህ ኑሩን ወሃቢስቶች ናቸው የገደሏቸው በማለት በጉዳዩ ላይ ገና ተጠርጥረው የተያዙ ግለሰቦችን ‹ቅጥረኛው ነፍሰ ገዳይ እና የሽብር ቡድኑ መሪ› በማለት ስማቸውን እየጠቀሰ ራሱ ከሶ ራሱ ፍርድ እዛው የሚሰጥ ነው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ግን እስከ አሁን ድረስ ጥፋተኛ ያልተባሉና ጉዳዩም ገና በሕግ ሒደት ላይ ያለ ጉዳይ ነው (በእስር ላይ በነበርኩበት ወቅት በዚህ ጉዳይ (‹የደምፃችን ይሰማ የደሴ ክንፍ አባላት› ተብለው) ተጠርጥረው ከታሰሩት አንዋር አደም እና አብዱ ያሲን ጋር ብዙ አውርተናል፤ ‹መንግስት ዜጎቹ ላይ ለምን ወንጀል እንደሚያቀነባብር አልገባንም;› ይሉኝ ነበር)፡፡ ዘጋቢ ፊልሙ የተለመደውን የሰለፊያ/ሱፊያ ክፍፍል ለማጉላት ከመሞከሩ ባለፈም አሁን ያለውን ‹የድምፃችን ይሰማ› እንቅስቃሴም ተጠያቂ ለማድረግ ይሞክራል፡፡
በመንግስታዊ ቴሌቪዥኑ የቀረቡት ከእስልምና እና ከሽብርተኝነት ጋር ተያይዘው በአራተኝነትና በአምስተኝነት ከቀረቡት ዘጋቢ ፊልሞች በግንቦት 2007 የቀረበው ‹የጥፋት መልዕክተኞች› እንዲሁም አሁን በጥር 2008 የቀረበው ‹የማንቂያ ደወል› ናቸው፡፡ ሁለቱም ዘጋቢ ፊልሞች በይዘታቸውም ሆነ በአላማቸው አንድ አይነት ሊባሉ የሚችሉ ናቸው፡፡
‹የዛሬዎቹ አክራሪዎች የሙሃመድ አብዱል ዋሃብ አስተምህሮ ከመጣ በኋላ ብቅ ያሉ ናቸው› ከማለት ጀምሮ፤ ‹የአክራሪዎቹ መፅሃፍት ሊቃጠሉ ይገባል› በማለት ስነ መለኮታዊ ብይን የሚሰጡ ናቸው፡፡ ሁለቱም ዘጋቢ ፊልሞች በ ‹ሀዘን ለመድረስ … ጉዞ ወደ ደሴ› ዘጋቢ ፊልም ላይ ዋነኛ የትኩረት ነጥብ የነበሩትን ሸህ ኑሩ ይማምን የአክራሪነት ሰለባ በማድረግ ያቀረቡ ሲሆን፤ ከአዲስ ግንባር እና ከጅሃዳዊ ሐረካት ዘጋቢ ፊልሞች ላይ ምስሎችን በመውሰድ ሒደቱ የቀደምቶቹ ዘጋቢ ፊልሞች ቀጣይ ክፍል የሆነ ያክል እንዲሰማን ያደርጋሉ፡፡ በአጭሩ ሁለቱም ዘጋቢ ፊልሞች ‹መንግስት በሐይማኖታዊ ጉዳይ ጣልቃ አይገባም› ከሚለው ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ በተቃራኒው መንግስት ለዜጎች ይህኛው ሴክት› ይስማማችኋል ወደ ሚል ምርጫ የገባባቸው ሆነው ነው የቀረቡት፡፡
በአጠቃላይ አምስቱ ዘጋቢ ፊልሞች በተመሳሳይ ድምፀት፣ አስፈሪ እና አስገምጋሚ ማጀቢያ ሙዚቃዎችን ከጀርባቸው አድርገው፤ እጅግ ተቃራኒ የሆኑ ግለሰቦችን በአንድ ቅርጫት በመክተት የሚፈርጁ ከመሆናቸውም ባለፈ በዜጎች ላይ ፖለቲካዊ ብይን በመስጠት ሙስሊሙን የበለጠ ግራ መጋባት ውስጥ የሚከቱ እንዲሁም ሙስሊም ያልሆነውን ሕብረተሰብ ደግሞ ፍርሃትና ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገባ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ በድምሩ 224 ደቂቃ የሚረዝሙት እነዚህ ዘጋቢ ፊልሞች ስለመንግስት ፍላጎት እና ሕብረተሰቡ ውስጥ ሊፈጠር ስለሚችለው ውዝግብ ብዙ የሚናገሩ ናቸው፡፡ መሰረታዊዎቹን እንኳን ብናይ፡
ሱፊያን ማጉላት – ሰለፊያን ማጠልሸት
ሁሉም ዘጋቢ ፊልሞች በአጭሩ የሚገልፁትን ነገር ቢኖር ነባሩ እስልምና (ሱፊያው) መቻቻልን የሚሰብክ እንደሆነና መጤው ዋሃቢያ (ሰለፊያ) ደግሞ ሃገሪቱን ወደ ትርምስ ለመክተት ሙስሊሙንም ወደ ተሳሳተ አቅጣጫ እየመሩት ስለሆነ ሰለፊያውን መፅሃፋቸውን ሳይቀር በማቃጠል ማስቆም አለብን የሚል ነው፡፡ እኔ ያገኝኋቸው የዘጋቢ ፊልሞቹ ሰለባዎች ‹ሱፊ ነኝ› – ‹ሰለፊ ነኝ› ሲሉ አልሰማሁም ሁሉም ‹ሙስሊም ነኝ› ይሉኛል እንጂ፡፡ ከዘጋቢ ፊልሞቹ ግን የአሁኑ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመብት እንቅስቃሴ አደባባይ ከመውጣቱ በኩል መንግስት በተለያዩ የፖሊሲ ሰነዶቹ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለን የእስልምና አክራሪነት መገለጫ ‹ሃዎርጅያ› የተባለው የእስልምና ሴክት ነው የሚለውን የቀድሞ ፍረጃውን ትቶ አሁን ነገሮችን በማስፋት ሰለፊያው (ውሃቢያው) ነው የአክራሪነቱ ሁሉ መገለጫ ወደሚል አጠቃላይ ፍረጃ እንደገባ መገንዘብ ይቻላል፡፡
የሱፊን አስተምሮ ድጋፍ በመስጠት ማጎልበት የሽብርተኝነት ዋነኛ መዋጊያ መሳሪያ እንደሆነ እንደ RAND Corporation እና Heritage Foundation ባሉ የአሜሪካ ፖሊሲ አማካሪዎች መገለፅ ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ ከሞሮኮእስከ ሩሲያ – ከአልጀሪያ እስከ ፓኪስታን ድረስ ይሄን መመሪያ የመከተል አዝማሚያ እንደሚታይ የቅርብ ጊዜ ሂደቶች ያመላክታሉ፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት እየተጠቀሰ ያለው የሱፊው አስተምህሮ መቻቻልን የበለጠ ይሰብካል ከሚል መነሻ እንደሆነ ይገልፃሉ፡፡ ይሄን ጉዳይ በጥልቀት ያጠኑት የበትለር ዩንቨርስቲው ዶ/ር ፌት ሙይዲን በቅርቡ በፃፉት አንድ ፅሁፋቸው ላይ፡
Promoting Sufism, particularly at the expense of other Islamic traditions is highly problematic. The perception of Sufism as […] a moderate or tolerant form of Islam cements a dichotomy between ‘good’ and ‘bad’ understanding of religion. […] Categorization of good and bad Muslims rely not on sound judgments of behaviors and actions but, rather on simple labels based on the way in which people practices their faith.
በማለት ‹ሱፊያው መልካም ነው፤ ሌላው ደግሞ ጥፋት ነው› የሚል የእስልምና አረዳድ በጣም አደገኛ እንደሆነ ይገልፃሉ፡፡ Mark Woodward et al በበኩላቸው ‘Salafi Violence and Sufi Tolerance? Rethinking Conventional Wisdom’ በተባለና ደቡብ ምስራቅ እስያንና ምዕራብ አፍሪካን እንደማሳያ በማድረግ ባዘጋጁት ጥናታዊፅሁፋቸው ከዚህ የዶ/ር ፌት ሙይዲን ሐሳብ ጋር ተመሳሳይ በሆነ መንገድ ‹ሰለፊያው ጦረኛ ነው፤ ሱፊያው ሰላማዊ ነው› የሚለው አካሄድ ከእውነታው የራቀ እንደሆነ እና ስነ መለኮታዊ ልዩነትን መሰረት ያደረገ አካሔድም የባሰ ችግርን እንጂ መፍትሔን እንደማይወልድ ይገልፃሉ፡፡ ዶ/ር ፌት ሙይዲን ጉዳዩን በሚገባ አጥንተው በፃፉትና ብዙ ተቀባይነት ባገኝው ‘Sponsoring Sufism: How Governments Promote Mystical Islam in their Domestic and Foreign Policy’ በተባለው መጽሃፋቸው በተለይም አንባገነናዊ መንግስታት ሱፊያውን ደግፈው የሚቆሙባቸው ሁለት ዋነኛ ምክንያቶች አሉ በማለት ያስረዳሉ፡
ሱፊያው ማሕበረሰብ በባሕሪው ከፖለቲካ ራሱን ያራቀ (apolitical) በመሆኑ አንባገነናዊ መንግስታቱ ፀጥ ለጥ አድርገው ለመግዛት ይቀላቸዋል እንዲሁም፤
እስልምና በዋናነት ከሚታወቅበት ካሕን አልባነት (non-clergical) በተለየ መልኩ የሱፊ የሐይማኖት አባቶች በሱፊያው ማሕበረሰብ ውስጥ ሰፊ ተቀባይነት ያላቸው በመሆናቸው እና ማሕበረሰቡንም ከፖለቲካ እንዲርቅ ማድረግ በቀላሉ ስለሚችሉ ነው በማለት ያስረዳሉ፡፡
በመንግስታዊው ቴሌቪዥን የቀረቡትን አምስቱንም ዘጋቢ ፊልሞች የተመለከተ ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ ሱፊያን ለማጠናከር መንገድ የመጥረግ ስራ እየተካሔደ እንደሆነ ሊሰማው ይችላል፡፡ ከአሁኑ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመብት እንቅስቃሴ ጋር ስማቸው በመጥፎ ከሚነሱት ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆኑት እስራኤላዊው ፕሮፌሰር ሐጋይ ኤርሊኸ ከአስር ዓመት በፊት ከሙስጠፋ ካባ ጋር በመሆን በ International Journal of Middle East Studies ላይ ‘Al-Ahbash and Wahhabiyya: Interpretations of Islam’ በሚል ርዕስ ባሳተሙት ፅሁፋቸው የኢትዮጵያንና የሊባኖስን መመሳሰል ተመልክተው በመደምደሚያቸው ላይ እንደ አህባሽ ያሉ የሱፊ አስተምህሮቶች እንዲጎለብቱ ቢደረግ መልካም እንደሆነ በገደምዳሜ ገልፀው ነበር፡፡ የዘጋቢ ፊልሞቹ መደምደሚያም ከዚህ እውነታ ጋር ይቀራረባል፤ ዶ/ር ፌት ሙይዲን በሚገልፁት መልኩ የሚሔድ መሆኑም ፍንትው ብሎ ይታየናል፡፡ ዶ/ር ሙይዲን ግን ‹ይህ በጣም አደገኛ አካሔድ ነው፤ ተጠንቀቁ!› እያሉ ነው፡፡
የመብት ጥያቄን መሸሽ
ሌላው የዘጋቢ ፊልሞቹ መሰረታዊ ባህሪ ለመንግስት ያልተመቹትን ሁሉንም አይነት እንቅስቃሴዎች በስመ ሙስሊም በአንድ ቅርጫት ውስጥ መክተታቸው ነው፡፡ ይሄም በተለይም ላለፉት አራት ዓመታት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች እያደረጉት ያለውን እጅግ ሰላማዊና ፍትሃዊ ጥያቄ በዘጋቢ ፊልሞቹ ከነአልቃይዳ እና አልሸባብ ጋር አንድ ላይ ደምረው በማቅረባቸው የሚታይ ነው፡፡ ዜጎች ሕገ መንግስቱን ይዘው አደባባይ ወጥተው ሕግ ይከበርልን ሲሉ የሌለን ዓላማ ፈጥሮ አላማችሁ ሌላ ነው ማለት መብት ጥያቄን ላለመመለስ የሚደረግ ሙከራ ከመሆን ያለፈ ፋይዳ የለውም፡፡ ዜጎች በሕጋዊ መንገድ የጠየቁት ጥያቄ የማይመለስላቸውና መብታቸው የማይከበርላቸው ከሆነ ደግሞ መብታቸውን ለማስከበር መጣራቸው አይቀርም፡፡ የመብት ጥያቄን መንግስት በዘጋቢ ፊልም አጥላልቶ ማለፉ ዘላቂነት ካለመኖሩም ሌላ ለመብት ጠያቂዎቹ ክብር አለመስጠትም ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሚያመጣው አይታወቅም፡፡
‹የከሸፈ የሽብርተኝነት ትግል?›
መንግስት የመብት ጥያቄዎችን ከሃይልና ከሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎች ጋር አመሳስሎ በዘጋቢ ፊልሞቹ ማቅረቡ ከሁሉም በላይ የሚያመጣው መዘዝ ደግሞ፤ የሚባለውን አክራሪነትም ሆነ ሽብርተኝነትን ከመከላከል ይልቅ የሚያባብስ ተግባር መሆኑ ነው፡፡ የሙስሊሙ (መአኮ) አባላት በተደጋጋሚ እንደሚሉት አክራሪነትንም ሆነ ሽብርተኝነትን መከላከል የሚቻለው ከሕዝቡ ጋር አብሮ በመስራት እንጂ መብትን የጠየቀን ሁሉ ‹አሸባሪዎች ናችሁ› በማለት አይደለም፡፡ ሽብርተኝነትን በእጅጉ የሚፀየፉትን እንደ የኮሚቴው አባላት ያሉ ሙስሊሞችን ‹ከአልሸባብ አባላት ጋር አንድ ናችሁ› ብሎ ፈርጆ ሽብርተኝነትን እታገላለሁ ማለት መቼም ፍሬ የሌለው ስራ ከመሆን አያልፍም፡፡ መንግስት አሁን የያዘው ሁሉንም ተቃውሞ በሽብርተኝነት የመፈረጅ አባዜ እጅግ ብዙ ዋጋ የሚያስከፍል ጦስ ይዞ መምጣቱም አይቀርም፡፡
Guilty until proven Innocent
ሌላው የዘጋቢ ፊልሞቹ ተመሳሳይ ባህሪ ደግሞ በፍርድ የተያዙ ጉዳዮችን ያለምንም ሐፍረት ብይን መስጠታቸው ነው፡፡ መንግስታዊው ቴሌቪዥን አሸባሪዎች ናቸው ብሎ በመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴው አባላት ላይ ውሳኔ የሰጠው ገና ዓቃቤ ሕግ ክስ በከፈተ በሁለተኛው ወር ላይ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ውሳኔ የሰጠው ግን መንግስታዊው ቴሌቪዥን ከወሰነባቸው ከሁለት ዓመት ከሰባት ወራት በኋላ ነው፡፡ ፍርድ ቤቱም የመንግስትን ውሳኔ ቀድሞ እያወቀ ነፃ ናቸው ብሎ ለማሰናበት ምንም አቅም አይኖረውም፡፡ ይሄን ተገንዝበው የመአኮው አባላት እነሱን አስመልክቶ የተላለፈውን ‹ጅሃዳዊ ሐረካት› የተባለው ዘጋቢ ፊልም እንዳይተላለፍ ከፍርድ ቤት እግድ (injunction) አውጥተው ቢሔዱም ማንም ሊሰማቸው አልፈቀደም፡፡ በደንብ ከሚታወቀው ከመአኮው ሒደት ባለፈም የሸህ ኑሩ ይማም ገዳዮች ናችሁ የተባሉ ግለሰቦችም በብሔራዊ ቴሌቪዥኑ ቅጥረኛ ነብሰ ገዳይ እና ሽብርተኞች ተብለው ከተፈረጁ ሁለት ዓመታት ቢያልፉም ይህ ፅሁፍ እስከተፃፈበት ጊዜ ድረስ ፍርድ ቤት ጥፋተኛ ያላላቸውና ጉዳያቸውም በፍርድ ቤት የተያዘ ጉዳይ ነው፡፡
በዘጋቢ ፊልሞቹ ገና ጉዳዩ ፍርድ ቤት በር እንደደረሰ የሚሰጠው ይህ የጥፋተኝነት ውሳኔ በአጠቃላይ በፍርድ ቤት የተያዘን ጉዳይ በሚዲያ ማራገብ ከሚያመጣው ተፅዕኖ ባለፈ እንደኛ አይነት የፍርድ ቤት ነፃነት በስራ አስፈፃሚው ጉያ ውስጥ ባለ ሀገር ደግሞ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ነፃ ይሆናል ብሎ ማሰብ ራስን ማድከም ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ይህ አይነቱ ፍረጃ ዜጎች ጥፋተኝነታቸው እስኪረጋገጥ ድረስ በሕግ ፊት ጥፋተኛ ተብለው ያለመገመት (presumption of innocence until proven guilty) ሕገ መንግስታዊ መብትን በመጣስ፤ በተገላቢጦሹ ራሳቸው ንፅህናቸውን እስኪያረጋግጡ ድረስ ጥፋተኛ ናቸው (presumption of guilty until proven innocent) ወደሚል መደምደሚያ ያደርሰናል፡፡
በሙስሊሙ ውስጥ ያለውን የስነ መለኮት መሰነጣጠር መጨመር
ኢትዮጵያ በሙስሊም ሕዝብ ብዛት በዓለም ላይ ካሉት ቀዳሚ አስራ አምስት ሀገራት አንዷ ስትሆን በሕዳጣን ሙስሊሞችም ረገድ በዓለም ላይ ከሕንድ ቀጥላ በሁለተኝነት ብዙ ሙስሊሞች ሕዳጣን (largest minority) ሆነው የሚኖሩባት አገር ናት፡፡ በዚህ ትልቅ ማሕበረሰብ ውስጥ የስነ መለኮታዊ ልዩነቶች መኖራቸው ባይካድም በብሔራዊ ቴሌቪዥኑ እየቀረቡ ያሉት የዘጋቢ ፊልሞች (በተለይም ‹የጥፋት መልዕክተኞች› እና ‹የማንቂያ ደወል› በተባሉት ዘጋቢ ፊልሞች) ግን ልዩነቱን የበለጠ በማጉላት በሙስሊሙ ማህበረሰብ ውስጥ ልዩነቶቹ የጎሉ እንዲሆኑ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ መንግስት በዘጋቢ ፊልሞቹ አንዱን ሴክት ደግፎ ሌላኛውን ማጣጣሉ ሙስሊሙ እርስ በርስ ከሱፊያ – ሰለፊያ ውዝግብ ባለፈ ትናንሽ ልዩነቶችን እያነሳ እንዲጠቋቆም በር የከፈቱ ናቸው፡፡ ‹ይሄ ሽርክ ነው›፣ ‹ይሄ ቢድኣ ነው› የሚለውን ፍረጃ በጥቃቅን ጉዳዮች ላይ ሳይቀር መሰማት የጀመሩበት ጊዜ ነው አሁን፡፡ በሙስሊሙ ዓለም የሚገኙት ስነ መለኮታዊ ልዩነቶች ሁሉ ዛሬ በመፅሃፍት፣ በሶሻል ሚዲያ እንዲሁም በሌሎች የመገናኛ መሳሪያዎች ላይ በርከት ብለው ለኢትዮጵያ ሙስሊም በገበያ ላይ ቀርበውለታል፡፡ ኢኽዋን፣ ተብሊግ፣ ሰለፊ፣ ዋሃቢ፣ ተክፊር፣ መደኺላ፣ሐዳዲያ፣ አህባሽ፣ ተብዲዕ፣ ተፍሲቅ፣ ተድሊል፣ ኻዋሪጅ፣ ሺዓ፣ ሱፊያ፣ ቀደሪያ፣ ሙዕተዚላ፣ ሙርጂት፣ አሕመዲያ፣ ማቱርዲያ፣ አሻሪያ፣ ከራሚ፣ ጀኸሚ፣ ቲጃኒ … እያለ የማያልቅ ስም መሰጣጣትና ፍረጃው በርትቷል፡፡ መንግስት በዘጋቢ ፊልሞቹ የመጡበትን የመብት ጥያቄዎች ከመመለስ ይልቅ ይሄን ክፍፍል ማጉላትን እንደ ግብ በመያዝ ነገ ሌላ ፈተናን ይዞ መጣ ዘንድ ዛሬ የተመቻቸ ሜዳ እያዘጋጀለት ይገኛል፡፡
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ሙስሊም የመብት ጥያቄ እንዲሁ መንግስት በዘጋቢ ፊልም አጥላልቶት የሚያልፍ እንዳልሆነ ያለፉት አራት ዓመታት ጥሩ ምስክሮች ናቸው፡፡ መንግስት ለተደራጀ የሰላማዊ ተቃውሞ ተገቢ ምላሽ ለመስጠት አሻፈረኝ ባለ ቁጥር ችግሮቹ የበለጠ እየተባባሱ የሀገሪቱን ፈተና የበለጠ ያንሩታል፡፡ ይባስ ብሎም ችግሩ ላይ ሌላ ችግር እየጨመረ ሕዝበ ሙስሊሙን የበለጠ ግራ መጋባት ውስጥ ሲከተው – ሙስሊም ያልሆነውን የሌላ እምነት ተከታይም የበለጠ ፍርሃት ውስጥ እያስገባው ነው፡፡

The post የኢትዮጵያ ሙስሊም ፈተና በ224 ደቂቃዎች (በዘላለም ክብረት) appeared first on Zehabesha Amharic.

ፍካሬ ዜና: o ባሳለፍነው ሳምንት የግል ባንኮች ድንገተኛ የብር እጥረት ውስጥ እንደገቡ ታወቀ o ረሀቡ ህፃናትን እየፈጀ ነው o በተለያዩ አካባቢዎች ሕዝባዊ አመጽ እንደቀጠለ ነው

0
0

oፍኖተ ዴሞክራሲ ራድዮ  አጫጭር ዜናዎች

o ረሀቡ ህፃናትን እየፈጀ ነው፡፡
o በተለያዩ አካባቢዎች ሕዝባዊ አመጽ እንደቀጠለ ነው፡፡
o ባሳለፍነው ሳምንት የግል ባንኮች ድንገተኛ የብር እጥረት ውስጥ እንደገቡ ታወቀ፡፡
o የድንበር ማካለሉ በዚህ በያዝነው አመት እንደሚጠናቀቅ በሱዳን እየተነገረ ነው፡
o ከሙስሊሞች እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ የታሰሩት ተፈረደባቸው
o ወያኔ በአሜሪካ የሚኖሩ ተቃዋሚዎች ተላልፈው እንዲሰጡት ለአሜሪካ ሰነድ እንዳዘጋጀ ተወቀ፡፡ o የወያኔ የመዋጮ ወረርሽኝ ሠራተኞችን እያማረረ ነው
o የአውሮፓው ፓርላማ ውሳኔዎችን አሳለፈ
o የቀድሞ የናይጄሪያ ባለስልጣኖች 9 ቢሊዮን የአገሪቷን ሀብት መዝረፋቸው ተነገረ
o የደቡብ ሱዳን የአንድነት መንግስት እንዲመሰረት የተያዘለት ቀነ ቀጠሮ ሳይከበር ቀረ

  •   ባሳለፍነው ሳምንት በሐዲያ ወደ ሆሳዕና እና ወደ ተለያዩ ከተሞች የሚደረጉ የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች ለአንድ ቀን ዝግ ሆነው መዋላቸውንና በኋላም መጀመራቸውን ከአካባቢው ከተገኘው መረጃ ለማወቅ ተችሏል። ትራንስፖርት ሊቋረጥ የቻለው የአካባቢው ባለስልጣኖች የጣሉትን ተጨማሪ የቅጣት መመሪያ በመቃወም አሽከርካሪዎች አድማ በመምታታቸው ሲሆን መመሪያው የተነሳ መሆኑ ሲገለጽ የትራንስፖርት አገልግሎቱ የጀመረ መሆኑ ታውቋል። ከዚህ ጋር በተያያዘ በሃዲያ ዞን ከሚገኘው ከዎቻሞ ዪኒቨርስቲ ተይዘው የተወሰዱት 8 ተማሪዎች የት እና በምን ሁኔታ ላይ መሆናችው ስላልታወቀ ቤተሰቦቻቸው በከፍተኛ ሀሳብና ጭንቀት ላይ የወደቁ መሆናቸውን ከአካባቢው የተገኙ ዜናዎች ገልጸዋል። በዲላም ዩኒቨርስቲ ውስጥ ከተማሪዎቹ እኩል ቁጥር ያለው የአግአዚ ጦር ተሰማርቶ ጥበቃ እያካሄደ ሲሆን በተማሪዎቹ ላይ ከፍተኛ በደል ከመፈጸሙ ባሻገር የእጅ ስልኮቻቸውንም የቀማ መሆኑ ታውቋል።
  •   ጥር 11 ቀን 2008 ዓም በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች የጥምቀት በዓል በደመቀ ሁኔታ የተከበረ ሲሆን የአዲስ አበባ በዓል አከባበር ላይ በወያኔ የደኅነነት ኃይሎች ተጥለቅሎ እንደንበር ከስፍራው የመጣው ዘገባ ገልጿል። ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆነና የሲቪል ልብስ የለበሱ የወያኔ የደህንነት ተቀጣሪዎች አስተናባሪ የሚል ባጅ ደረታቸው ላይ ለጥፈው ታቦቱን አጅቦ ወደ መንበሩ ለማስገባት ከሚንቀሳቀሰው ሕዝበ

ጥር 15 ቀን 2008 ዓ.ም

dollar

ክርስትያን ጋር በመቀላቀል ሲያስፈራሩ የነበሩ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። በአዲስ አበባ እና በአካባቢዎ ባሉ አንዳንድ ቦታዎች ተቃውሞ የሚያሰሙ ወጣቶች የተደበደቡና ተይዘው የታሰሩ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን በተለያዩ ከተሞችም የጥምቀት በዓሉን አስታኮ በወያኔ አገዛዝ ላይ ተቃውሞ ሲሰማ መዋሉ ተነግሯል። በማግስቱ ጥር 12 ቀን 2008 ዓ/ም በአዲስ አበባ ተከብሮ በዋለው የቃና ዘገለሊላ በዓል ላይ የበዓሉ ታዳሚ በነበሩት ምዕመናንና በፖሊስ መካከል ግጭት ተነስቶ ለግዜው ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች በአካላቸው ላይ ጉዳት እንደደረሰባቸውና በፖሊስ ታፍነው የተወሰዱ መሆናቸውንም ከስፍራው የደረው ዘገባ ገልጿል። በተለምዶ ሾላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘውን የየካ ቅዱስ ሚካኤል ታቦትን በማጀብ ወደ መንበሩ ለማስገባት ተሰባስበው የነበሩ ምዕመናን ባህላዊ ዘፈኖችና ጭፈራዎች እያደረጉ በሚጓዙበት ወቅት ለጭፈራ ማድመቂያ የያዙትን ዱላ በተለያዩ ስፍራዎች ቆሞ ይጠብቅ የነበረው የወያኔ የፖሊስ ኃይል ለመንጠቅ ሙከራ ሲያደረግ ከፍተኛ ግብግብ መከሰቱና ዱላቸውን የተቀሙት ወጣቶች እንደጀመራችሁ ጨርሱን በማለት ፖሊሶችን ማጥቃት በመጀመራቸው ግጭት ተፈጥሮ በርካታዎች የመፈንከት አደጋ እንደደረሰባቸውና አንዳንዶቹ ሲሮጡ የእግር ወለምታ አጋጥሟቸው ጉዳት እንደደረሰባችው ተያይዞ የመጣው ዜና ይገልጻል። ብዙዎች ታስረው በመኪና ተጭነው ወደ አልታወቀ ቦታ የተወሰዱ ሲሆን ከፖሊስ አባላት መካከልም ጉዳት የደረሰባችው እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አሳሳቢነቱ እየጨመረ የሄደው ሊምፎማ በመባል የሚታወቀው በሰውነት ውስጥ የሚገኙ የሊምፍ አካላትን የሚያጠቃና የደም መበከልንና መመረዝን የሚያስከትለው በሽታ አርሶ አደር ገበሬዎችን በወረርሽኝ መልክ እያጠቃ መሆኑን ከሀኪሞችና በጤና ላይ ምርምር ከሚያካሄዱ ወገኖች መረዳት ተችሏል፡፡ ከጥቁር አንበሳና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታሎች ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባዎች ለህክምና የሚመጡ አብዛኛዎቹ ገበሬዎች ሊምፎማ በተባው በሽታ የተጠቁና የበርካቶቹም ሁኔታ ወደ የደም ነቀርሳነት ያደገ መሆኑን መገንዘብ ተችሏል፡፡ ይህ በሽታ ሊከሰት የሚቸው በዘር፣ ከቀዶ ህክምና በኋላ እንደ ጡት ነቀርሳ የመሰለው፣ ጡቱ በቀዶ ህክምና ከተወገደ በኋላ የተለመደ ሲሆን በአረም ማጥፊያ አሲድም ሊከሰት እንደሚችል ይታወቃል፡፡ እንዲህ ያለውን በሽታ ሊያስከትሉ የሚችሉ የአረም ማጥፊያ አሲዶችን ከይዘታቸው መለየትና እንዳይገቡ እግድ ማውጣት ሲገባ ወደ አገር ውስጥ በወያኔ የንግድ ድርጅቶች አማካይነት እንዲገቡ መደረጋቸውና ገበሬው በግዴታ እንዲገዛና እንዲጠቀም መደረጉ ለዚህ ለገዳዩ ሊምፎማ በሽታ እንዳጋለጣቸው ማወቅ ተችሏል፡፡ ይህ ደግሞ ለተቃውሞ የወጡ ዜጎችን ከመረሸን በላይም የከፋ መሆኑን ከፍተኛ የህክምና ባለሙያዎች በመቆጨት ያስረዳሉ፡፡

ከገሙ ላይቀር ብስብስ ነው እንዲሉ ወያኔን እንደ ጋማ ከብት እያገለገለ ያለው ኃይለማርያም ጥር 1 ቀን 2008 ዓ.ም. ከመንግስት ተብየው ካዝና ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት ልጁ ሀናን በቤተ መንግስት መዳሩ ታወቀ፡፡ ይህን ወጪ የሰርጉ እድምተኛ የነበረው የሳዑዲው ደላላ አላሙዲ ወጪውን ሙሉውን የሸፈነ መሆኑን ከቅርብ ምንጮች ተረድተናል፡፡ አስቀድሞ ከወያኔው ገንዘብ ሚንስትር የወጣውን ገንዘብ የወያኔ ቁንጮዎች ለመቀራመት እንዲያመቻቸው ወደ “መለስ ፋውዴሽን” የዘረፋ ቋት እንደሚገባ መወሰኑ ታውቋል፡፡ ይህ ሁኔታ በ1997 ዓ.ም. ሟቹ መለስ ዜናዊ የጋጠ ወጥ ልጁ የሰመሀልን 12ኛ ክፍል ማጠናቀቅ አስመልክቶ በሸራተን ሆቴል የነበረውን የውስኪ ግብዣ ያስታውሳል፡፡ የመለስ ልጅንም ወጪ የሸፈነው አላሙዲ መሆኑ በወቅቱ ይነገር እንደነበር ማስታወሱ ተገቢ ነው፡፡ ዘረኛ አምባ-ገነኖች በመጠሪያ ስማቸው ቢለያዩ እንጂ በምግባራቸው ያው እንድ ናቸው።

 

File Photo

File Photo

 በወያኔ መገናኛ ብዙሀን እስከ ዛሬ ድርቁን የዝናብ እጥረት፣ እርሀቡን የምግብ እጥረት በማለት በሕዝብ ስቃይና ሞት ላይ ለፖለቲካ ትርፍ ብቻ በማሰብ የቃላት ጨዋታ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡ እስካሁን ባለው መረጃ ከአምስት መቶ ሺ በላይ የተለያዩ ከብቶች በድርቁ ምክንያት እረግፈዋል፡፡ ህፃናት እርሀቡና ጥሙ ጠንቶባቸው ዋይ ዋይ እያሉ እንደዋዛ፣ እንደ ቅጠል እየረገፉ ነው፡፡ ወያኔ ነጋ ጠባ እያሰላ ያለው ከርሀቡ የሚገኘውን ትርፍ ነው፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት ከተለያዩ አገራት የተውጣጣ የህፃናት አድን ድርጅቶች ቡድን እርሀቡ ህፃናትን፣ ነፍሰጡርና የሚያጠቡ እናቶችን በከፍተኛ ሁኔታ እያጠቃ መሆኑን መገንዘብ ችለዋል፡፡ ህፃናትና ነፍሰጡር እናቶች በርሀቡና በጠኔው እየረገፉ ነው፡፡ የርሀቡን አስከፊነትን የታዘበው የህፃናት አድን ድርጅቶች ቡድን በመጨረሻ ያሰማው 1.4 ቢሊዮን ዶላር በአስቸኳይ ከለጋሽ አገራትና ከግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ማግኘት ካልተቻለ የርሀቡ ግድያ ከመልቀም ወደ ማጨድ ሊሸጋገር እንደሚችል ስጋታቸውን ሰንዝረዋል፡፡ ከዚህ ከተጠየቀው የገንዘብ መጠን መገንዘብ የሚቻለው እርሀቡ እጅግ ዘግናኝና ከግምት በላይ እንደሆነ ነው፡፡ በርሀብ አለጋ እየተገረፉ ያሉትን ገበሬዎች የወያኔ የንግድ ድርጅቶች የማዳበሪያ እዳ ከርሀቡ የተረፉ ከብቶቻቸውን ሽጠው እንዲከፍሉ እያስገደዷቸውና እያንገላቷቸው መሆኑን አውቀናል፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች የማዳሪያ እዳ ያልከፈለ አባወራ እርዳታ እንዳይሰጠው መታገዱ ይታወቃል፡፡ በንጉሡ ዘመን ድርቅ ሰብሉን ክው አድርጎ አድቆት ያዘረዘረው እንኳ ከአፈር ተደባልቆ እየታየ ባለ እርስቶቹ ገበሬው የግድ እንዲገብር ያስገድዱት እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ ይህንን ግፍ ወያኔ ደገመው፡፡ እርሀቡ አድማሱንና መከራውን እያሰፋ ነው፡፡ ወያኔ ደግሞ ከረሀቡ የፖለቲካና የገንዘብ ትርፉ ለማካበት እየማሰነ ነው፡፡

በተያያዘ ዜና ካሪታስ ኢንተርናሽናል የተባለው የካቶሊክ የአርዳታ ሰጭ ድርጅት ባለስልጣኖችን በወቅቱ እርዳታ ካልተኘ በኢትዮጵያ በዚህ ዓመት መጨረሻ ላይ ከፍተኛ የሆነ እልቂት ሊከተል እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። ድርቁ ባጠቃቸው አካባቢዎች ከ90 ከመቶ በላይ በመቀነሱ ምክንያት በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ በድርቅና ረሃብ እየተጠቃ መሆኑን ባለስልጣኖቹ ገልጸው ካሁኑ ጀምሮ በእርዳታው ላይ መረባረብ ካልተቻለ የዛሬ ሰላሳ አመት ተፈጥሮ የነበረው ዓይነት የእልቂት ሁኔታ ሊደገም እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።

በሌላ በኩል ለእርዳታ የመጣውን እህል በተለያየ መንገድ በመዝረፍ ላይ ያሉት የወያኔ ባለስልጣኖች ሕዝቡን እያስመረሩት መሆኑ እየተስተዋለ ነው። በዚህ ሳምንት ባገኘነው ዜና መሰረት በመቂና በሞጆ ከተሞች መካከል በሚገኝ የህብረት ስራ ማህበር መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ የነበረ ስንዴ ጨለማን ተገን በማድረግ አስራ አምስት በሚሆኑ በበቅሎ በሚጎተቱ ጋሪዎች ተጭኖ ወደ ጥቁር ገበያ ለሽያጭ ሲወጣ የተመለከቱ መሆናቸውን በአካባቢው የነበሩ የአይን እማኞች የገለጹ ሲሆን የስንዴው ብዛት እስከ ሁለት ሺህ ኩንታል ሊጠጋ እንደሚችል ተናገረዋል። ድርቅና ረሃብ ያጠቃቸው ወገኖች እርዳታ በማጣታችው ወደ አዲስ አበባ እየፈለሱ መሆናችውም እየታየ ነው። ሰሞኑኑ ዘጋቢያችን በመርካቶ ራጉኤል ቤተክርስትያን አካባቢ ያነጋገራቸው ወገኖች ከትግራይና ከወሎ ቦረና የመጡ መሆናቸውን የገለጸሉት ሲሆን የእርዳታ ስንዴ እንሰጣችኋለን ከሚል ተስፋ በስተቀር የተሰፈረልን እህል ባለመኖሩ ልጆቻችን ሲሞቱ ከማየታችን በፊት በራችንን ዘግተን መምጣቱን መርጠናል ብለውታል።

  •   ወያኔ በማን አለብኝነት የደነገገውን የአዲስ አበባን የቆዳ ስፋት እሰከ አንድ መቶ ሃያ ኪሎ ሜትር ድረስ ለመለጠጥ መደንገጉን በመቃወም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎችና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ያለ ማቋረጥ በተካሄዱ አመጾች ወያኔ ለይስሙላ ድንጋጌው መነሳቱን ቢለፍፍም የተጀመረው አመጽን ሊገታው እንዳልቻለ የታወቀ ነው፡፡ ወያኔ በርካታ ህጻናትን፣ ወጣቶችን፣ ገበሬዎችን፣ ሴቶችን ገድሎ ሲያበቃ የማስተር ፕላኑ መሰረዙን ማውራቱ ለሕዝብ ያለውን ንቀት ሚያሳይ መሆኑን የፖለቲካ ተንታኞች ያስረዳሉ፡፡ ወደ አምስት ሺ የሚጠጉ ሰዎች በየእስር ቤቶች በግፍ እየማቀቁ ባለበት የማስተር ፕላኑ መሰረዝ ከፖለቲካ ቧልትነት አይዘልም የሚል አስተያየት እየተሰማ ነው፡፡ አሁን እየተካሄደ ያለው እንቅስቃሴ ወያኔ እራሱን እንጂ ሕዝብን አያታልልም የሚል መንፈስ የተላበሰ መሆኑን መገንዘብ ችለናል፡ ፡ የማስተር ፕላን መሰረዝ በግብር መገለጽ ይገባዋል የሚሉ ወገኖች እንደሚሉት የንፁሀንን ደም ያፈሰሱ የአጋዚ ጦር አባላት ለፍርድ ሲቀርቡና ቤተሰቦቻቸው ለተገደሉባቸው ቤተሰቦች ተገቢ የህይወት ካሣ ሲከፈል፣ የታሰሩት በአጠቃላይ ሲፈቱና ተገቢ ካሣ ሲከፈላቸው መሆኑን አበክረው ያስረዳሉ፡፡ ለዚህ ነው ሰሞኑን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ሕዝባዊ አመጹ እየቀጠለ ያለው፡፡
  •   በዚህ በዘረኛው ወያኔ ዘመን አብዛኛው ሥራ የሚከናወነው ጥናት ላይ ተመርኩዞ ሳይሆን እንዲሁ በደፈናው ነው፡፡ አንዳንዶች በጥናት ላይ እንደተመሰረቱ የሚነገርላቸው ቢሆኑም ዝም ብለው አረጋ ሰራሽ በመሆናቸው ጥናቱን አካሄደ የሚባለው ክፍል እራሱ መጠናት እንዳለበት የሚናገሩ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ባለፈው ሳምንት ምንጩ ከዓለም የገንዘብ ድረጅት የተገኘ ብድር እንደሆነ የሚነገር የውጪ ምንዛሪ በመገኘቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በድንገት በፋብሪካ ሥራ ለተሰማሩ ድርጅቶች ምንዛሪ እንደሚሰጥ በማሳወቁ የግል ብንኮች ላይ ከፍተኛ ቀውስ እንደፈጠረ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የባንክ ባለሙያዎች እንደሚሉት እንዲህ ዓይነቱ የግድየለሽነት አሰራር ከበስተጀርባው ተንኮል ያዘለ እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡ የባንኮችን በነፃነት የመፎካከር ሁኔታን በእጅጉ ያውካል፡፡ ለምሳሌ ከአንድ የግል ባንክ ብቻ በአንድ ቀን 1.3 ቢሊዮን ብር እንዲወጣ መደረጉ ለግል ባንኮች ከፍተኛ ፈተና መሆኑን ባለሙዎቹ ያስረዳሉ፡፡ በአንድ ቀን ከተለያዩ ባንኮች ወጪ ተደርጎ ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲገባ የተደረገው ገንዘብ 4.5 ቢሊዮን ብር ሲሆን ይህን ያህል ገንዘብ በአንድ ጊዜ ማውጣት የባንኮቹን እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ እንዳወከው ተውቋል፡፡

ethiopia sudan Boarder

  •   ወያኔ በተደጋጋሚ ከሱዳን ጋር ምንም ዓይነት ድንበርን ለማካለል የተካሄደ ድርድር መኖሩን ቢክድም በሱዳን በኩል ግን በማስረጃ እየቀረበ መሆኑን መረዳት ተችሏል፡፡ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር 725 ኪሎ ሜትር እርዝመት ያለው ድንበርተኛ መሆኗ ታወቃል፡፡ ወያኔና የአል በሺር መንግስት በሟቹ በመለስ ዜናዊ ትዕዛዝ ከሁለቱ አገራት የተውጣጣ ጉዳዩን የሚያጠና የቴክኒክ ቡድን ተመስርቶ አንደነበር የሱዳኑ ጋዜጣ “ሱዳን ትሪቡን” የተሰኘው ዘግቧል፡፡ ይህ የተጀመረው ጥናት እንዲቀጥል አል በሺር 2014 ዓ.ም. የወያኔ የይስሙላውን መሪ ኃይለ ማርያምን ማሳሰቡን አስታውሷል፡፡ ሱዳን ከኢትዮጵያ ይገባኛል የምትለው መሬት ሰቲት፣ አትባራ እና ባላሳም የተባሉ ወንዞች የሚፈሱበት 600 ሺ ሄክታር ስፋት

ያለው፣ እየታረሰ ያለ ለም መሬትን አንደሆነ ጋዜጣው አትቷል፡፡ ይህ ቦታም ለገደሀሪፍ አዋሳኝ የሆነ ሲሆን አል-ፋሻጋ በመባል የሚታወቅ እንደሆነም ሱዳን ትሪቡን ጠቁሟል፡፡ ይህ የተጠቀሰው ስፋት የአዲስ አበባን ስፋት ከአስር እጅ በላይ እንደሚያጥፍ የስነ-ምህዳር አዋቂዎች ያስረዳሉ፡፡ ወያኔ አገር አጥፊ ነው ሲባል አገርን ይሸጣል ማለት ነው፡

  •   “ድምጻችን ያሰማ” የሚሉ ሕዝበ ሙስሊሙ በወያኔ ላይ በአንድነት እንዲነሳ የሚቀሰቅሱ ጽሑፎችን በትነዋል፣ የታሰሩትን የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን ለማስፈታት ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ 16 የእስልምና እምነት ተከታዮች ተፈረደባቸው፡፡ ማክሰኞ ጥር 10 ቀን 2008 ዓ.ም. የወያኔ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 14ኛ ወንወጀል ችሎት በተከሳሾቹ ላይ እጃቸው ከተያዘበት አንስቶ የሚታሰብ 7 አመት ጽኑ እስራት ፈረደባቸው፡፡ ተከሳሾቹ 15 ወንዶችና አንዲት ሴት ሲሆኑ እነሱም ኤልያስ ከድር፣ ሙባረክ ከድር፣ ቶፊቅ መሐመድ፣ ፌይሰል አርጋው፣ አብዱልመጂድ አብዱልከሪም፣ እስማኤል ሙስጠፋ፣ ሬድዋን አብደላ፣ አንዋር ሱልጣን፣ አብዱላዚዝ ፈቱዲን፣ ጃፋር ደጋ፣ ፋሩቅ ሰይድ፣ መሪም ሀያት፣ መሐመድ አሊ፣ መሐመድ አይለየን፣ አክበር ስልጣን እና ሙአዝ ሙደሲር ናቸው፡፡ የወያኔው አቃቤ ህግ ያተተባቸው በአዲስ አበባና በወልቂጤ፣ የታሰሩትን የሙስሊሙ ህብተሰብ ችግሮችን ለመፍታት የተቋቋመው ኮሚቴ አባላት፣ በወያኔ በመታሰራቸው እነሱን ተክቶ ለመሥራት በህቡዕ በመንቀሳቀሳቸው እንደሆነና በየመስጂዱ ውስጥ ውስጡን ሕዝበ ሙስሊሙ በወያኔ ላይ እንዲያምጽ በመቀስቀሳቸው በመሆኑን አትቷል፡፡ ወያኔ በየጊዜው ሙስሊሞችን ያስራል ትግላቸው ግን እንደቀጠለ ነው፡፡ ይህ የሙስሊም ኢትዮጵያውያንን ትግል ሕዝበ ክርስቲያኑም እንደሚደግፈው የታወቀ ነው፡፡

muslim addis

  •   ወያኔ በአሜሪካ የሚኖሩ ተቃዋሚዎችን አድኖ ወደ ሀገር ቤት የአሜሪካ መንግስት እንዲልክለት እረቂቅ ሰነድ አዘጋጅቶ ማጠናቀቁን ከውስጥ አወቆች መረዳት ተችሏል፡፡ ከዚህ ቀደም በሌሉበት እስራት የፈረደባቸውና በ”ሽብርተኝነት” የወነጀላቸውን ሁሉ አሜሪካ እያሰረች እንድትልክለት መሆኑን ከሰነዱ መረዳት እንደሚቻል እነዚሁ ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ ይህ ድርጊት አወቅሽ አወቅሽ ሲሏት መጽሐፍ አጠበች እንደሚባለው ያለ መሆኑን የሚገልጹ የዓለም አቀፍ ህግ አዋቂዎች ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከወያኔ የደህንነት ምንጮች የተገኘው ጉዳዩ የሚያነጣጥረው በተለይ በኢሕአፓ አባላት ላይ እንደሆነና በተለያዩ ጊዜያት የተቃውሞ ሰልፎችንና ስብሰባዎችን በመምራትና በመስተባበር የሚታወቁትንም ያካትታል፡፡ በተለይ በአሜሪካ በወያኔ ኤምባሲ የወያኔን ባንዲራ አውርደው የኢትዮጵያ ባንዲራን የሰቀሉትን፣ በስብሀት ነጋና በሬድዋን ላይ የተቃውሞ ድምጽ ያሰሙት ተላልፈው እንዲሰጧቸው ከሚጠየቁት በመጀመሪያው እረድፍ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡
  •   ደርግን በመዋጮ ብዛት ይኮንነው የነበረው ወያኔ መዋጮ በግዳጅ የሠራተኛውን ጉሮሮ እያነቀ በመውሰድ ተወዳዳሪ አልተገኘለትም፡፡ የዓባይ ግድብ መዋጮ አላቆም በማለቱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በመርገምነቱ እንጂ በሲሳይነቱ መታየት አቁሟል፡፡ ከዚህ ከጥር ወር ጀምሮ የሚቀቆረጠው የጤና

መድንም እዬዬ እያሰኘ ነው፡፡ ህክምና ወደ ሸቀጥነት በወረደበት አገር በገንዘብ ያልተገኘ ህክምና በመድንማ ዘበት እንደሚሆን የተፈታ ህልም ነው፡፡ አብዛኛው ሰው እንደሚለው ወያኔ በመድን ስምም የሚሰበስበው ለዛው ለመከረኛው ዓባይ ገድብ እንደሆነ ነው፡፡ የዛሬ አስር ወር ግድም ወያኔ ምርጫ ተብዬውን አስታኮ የደሞዝ ጭማሪ እንደሚያደር ቀለምዶ ሲያበቃ እንኳን ጭማሪው ወሬውም የለም፡፡ ሠራተኛው እንዳይተፍስ በስብሰባ ስም አበል እየፈለ አፉን ማስያዝ የሚል ዘመቻ ተይዟል፡፡ የወያኔ አባላትም በተጣለባቸው የግዴታ የአባልነት መዋጮ እየተማረሩ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ከዚህ ቀደም በፈቃደኝነት ከ50 እስከ መቶ ብር ይከፍሉ የነበረው ቀርቶ በደሞዝ መክፈያው ላይ በመትከል አራት ከመቶ ከደሞዛቸው እንዲቆረጥ በመወሰኑ ቅሬታቸውን በማልጎምጎም እየገለጹ መሆኑንም ተረድተናል፡፡ የውሀ፣ የመብራት ታሪፍ በቅርቡ ጨምሯል፡፡ በተመሳሳይ መልኩም የዕለት ተዕለት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ እየናረ ይገኛል፡፡

 ባለፈው ሳምንት የአውሮፓው ህብረት ምክር ቤት (ፓርላማ) ሰሞኑን በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን የሕዝብ አመጽ አንተርሶ ጠንካራ ውሳኔዎች ማስተላለፉ ተገለጿል። የአውሮፓው ሕብረት ምክር ቤት ባለፉት ሁለት ወራት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን በመቃወም ተካሄዱትን ሕዝባዊ አመጾች ለመግታት ወታደሮች ከ140 ሰዎች በላይ መግደላቸውን፤ የአዲስ አበባ መስፋፋት ብዙ አርሶ አደሮችን ያፈናቀለ መሆኑን፣ በአካባቢው የሰብአዊ መብት ጥሰት መኖሩን፤ የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች አሸባሪዎች ናቸው በሚል በርካታ ሰልፈኞችን ማሰሩን፤ የፖለቲካ ድርጅቶች መሪዎችን ጋዜጠኞችንና ጦማሪያንና ይዞ እያሰቃየ መሆኑና አንዳንዶቹንም በሽብረተኞች ክስ በማፈረድ በእስር ቤት ማሰቃየቱንና በአንዳንድ አካባቢዎች የሚያካሄደው ጦርነትና ጭፍጨፋ አስከፊ መሆኑን የተረዳ መሆኑን ገልጿል። በተጨማሪ የወያኔ አገዛዝ ባለፈው አመት ግንቦት ወር ላይ ያካሄደው ምርጫ በአፈናና በማስፈራራት የተካሄደ መሆኑና አርሶ አደሮች ለም ከሆነው መሬታቸው ላይ ተነቅለው መሬታቸው ለባዕዳን መሰጠቱን ምክር ቤቱ መረጃ የደረሰው መሆኑን በመጠቆም ጉዳዩ ያሳሰበው መሆኑ አብራርቷል። ወያኔ በሕዝብ ላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ መብት ረገጣና አፈና እያካሄደ በየአመቱ 3 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገንዘብ ማግኘቱ አግባብ አለመሆኑን ምክር ቤቱ ገልጾ በርካታ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።፡ በውሳኔውም ኦሮሚኛ ተናጋሪዎች በሚኖሩበትና በሌሎች የኢትዮጵያ ግዛቶች የወያኔ ወታደሮች በዜጎች ላይ ያካሄዱትን ገደብ የለሽ ግድያ፤ የሰብአዊ መብት ረገጣ፤ ህገ ወጥ እስራትንና ሰቆቃዊ ድርጊቶች፤ የመናገርና የመጻፍ መብት መታገዳቸውን እንዲሁም ወንጀለኞች ለፍርድ ሳይቀርቡ በነጻ መለቀቃቸውን አውግዟል። በመንግስት የጸጥታ ወታደሮች እየተደረጉ ያሉት የአፍናና የግድያ ተግባሮች ባስቸኳይ እንዲቆሙና መብታቸውን በመጠቀም ድምጻቸውን በማሰማታቸው ብቻ የታሰሩ ተማሪዎች፤ አርሶ አደሮች የፖለቲካ ተቃዋሚዎች፣ ምሁራን ጋዜጠኞችና ጦማራውያን በሙሉ ባስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል። በተደረጉት ግድያዎች ላይ ነጻና ገለልተኛ በሆነ መንገድ ምርመራና ማጣራት እንዲካሄድና ጥፋተኞች ለፍርድ እንዲቀርቡ ጥሪ አስተላልፏል። ወያኔ የዓለም አቀፉንና የአፍሪካ ህብረትን የሰብአዊ መብት ቻርተርና ድንጋጌን ማክበር ያለበት መሆኑን ገልጾ በሚዲያ ላይ እያካሄደ ያለውን የሞገድ አፈናና እንዲያነሳና ነጻ የሆኑ ሚዲያዎች ስራቸውን በነጻ የሚሰሩበት ሁኔታ እንዲፈጠር ጠይቋል። አልአግባብ እየተካሄደ ያለው የሰፈራ

ፕሮግራም ምክር ቤቱን ያሳሰበው መሆኑን ገልጾ በአካባቢዎቹ የሚደረጉት የልማት ስራዎች ሕዝብ ጋር ተመካክሮና ተስማምቶ መሆን እንደሚገባው አሳስቧል። የአውሮፓ አገሮች ለልማት ስራዎች ለወያኔ የሚሰጡት እርዳታና ብድር ከአገሪቱ የሰብአዊ መብት ሁኔታ ጋር መመጣጠን ያለበት መሆኑን ገልጾ የአውሮፓው ኅባረትና አባል አገሮች በንጹሐን ዜጎች ላይ እየተወሰደ ያለውን ርምጃ ኮንነው ድርጊቱን ለማስቆም አስፈላጊውን ተጽእኖ እንዲያደርጉ ጥሪ አድርገዋል።

  •   የናይጄሪያ የማስታወቂያ ሚኒስትር ትናንት ሰኞ ጥር 9 ቀን 2008 ዓም ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በሰባት ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ የናይጄሪያ አገረ ገዠዎች፤ ሚንስትሮች የንግድ ተቋም ባለቤቶች ፤ የባንክ እና የመንግስት ባለሥልጣኖች 9 ቢሊዮን ዶላር የአገሪቷን ገንዘብ አለአግባብ የዘረፉ መሆናቸውን ገልጸዋል። የተሰረቀው ገንዘብ 1.35 ትሪሊዮን የናይጄሪያ ናይራ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸው ይህም 36 ሆስፒታሎች ለመስራት ወይም 4000 ተማሪዎችን እስከዩነቨርስቲ ድረስ ለማስተማር የሚያስችል ገንዘብ እንደነበር ገልጸዋል። ሁኔታው አሳሳቢ መሆኑን ገልጸው ባሁኑ ወቅት አስፈላጊው ርምጃ መወሰድ አለበት ብለዋል። ሚኒስትሩ የተዘረፈውን ገንዘብ ዝርዝር መረጃም አቅርበዋል። ገንዘቡ ተዘርፏል የተባለው እንደ አውሮፓ አቆጣጠር ከ2006 እስከ 2013 በአብዛኛው የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጉድላክ ጆናታን በስልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት ሲሆን የቀድሞ የጸጥታ አማካሪ የነበሩት ሚስተር ዳሱኪ 2 ቢሊዮን ዶላር ዘርፈዋል ተብለው መወንጀላቸው ይታወሳል። በአሁኑ ወቅት የናይጄሪያ ተቃዋሚ ፓርቲ የሆነው ፒፕልስ ዴሞክራቲ ፓርቲ የአሁኑ እርምጃ የፓርቲውን አባላት ለማጥቃት ሆን ተብሎ በስልጣን ላይ ባለው ኦል ፕሮግሬሲቭ ኮንግሬስ በተባለው ፓርቲ የተጠነሰሰ ሴራ የሚል ውንጀላ ሲያቀርብ ባለስልጣኖቹ ደግሞ የአገሪቱን ገንዘብ የሰረቀ የማንኛውም ፓርቲ አባል ለፍርድ ይቀርባል ብለዋል።
  •   በደቡብ ሱዳን ከሁለቱም ተጻራሪ ወገኖች በተውጣጡ ወኪሎች እንዲመሰረት ስምምነት ተደርሶበት የነበረው ጊዜያዊ የአንድነት መንግስት በተግባር እንዲውል የተሰጠውን ቀነ ቀጠሮ ያሳለፈ መሆኑ ተገለጸ። የአንድነት መንግስቱ እንዳይመሰረት እንቅፋት ከሆኑት አቢይ ምክንያቶች ውስጥ አንዱ የስልቫኬር መንግስት ከስምምነት ውጭ የአካባቢ አስተዳደሮችን ከ10 ወደ 28 ከፍ ማደረጉንና 28 አስተዳዳሪዎች መሾሙን በሪክ ማቻር የሚመራው የአማጽያን ኃይል በመቃወሙና ባለመቀበሉ መሆኑ ታውቋል። በዕቅዱ መሰረት ከሁለቱም ተጻራሪ ኃይሎች የተውጣጣ የአንድነት መንግስት ከጥር 13 ቀን 2008 ዓም በፊት መመስረት ነበረበት። ለስምምነቱ መፍረስ ሁለቱም ወገኖች እርስ በርሳቸው የተወነጃጀሉ ሲሆን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰሞኑን ባወጣው ዘገባ ሁለቱም ተጻራሪ ኃይሎች ጦርነቱን በማስፋፋት እንዲሁም በጦር ሜዳዎች የጅምላ ርሸና በማካሄድ፤ የያዟቸውን ዜጎች ዱካ በማጥፋት፤ በቡድን ሴቶችን በመድፈር፤ ለወሲብ አገልግሎት ሴቶች አግቶ በመያዝ ፤ አስገድዶ ጽንስን በማስወረድና የመሳሰሉ ወንጀሎችን በመፈጸም በኩል ሁለቱም ወገኖች ተጠያቂዎች ናቸው ብሏል።

 ባለፈው ሳምንት በምዕራብ ፓኪስታን በቻርሳዳ ከተማ በሚገኘው ባቻ ከሃን ዩንቨርስቲ ላይ ታጣቂዎች ባካሄዱት የቦምብ ጥቃት 19 ሰዎች መገደላቸውና ከ50 በላይ መቁሰላችወን የፓኪስታን ፖሊስ ገልጿል። አጥቂዎቹ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ተኩል ሲሆን የዩኒቨርስቲውን የጀርባ አጥር በመዝለል ጥቃቱን መሳሪያ በመተኮስና ቦምብ በማፈንዳት መፈጸማቸው የተገለጸ ሲሆን ከዩኒቨርስቲው የጸጥታ አባላት ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ተደርጓል። አንድ የታሊባን ወታደራዊ ኮማንደር ጥቃቱ የተወሰደው በታሊባን መሆኑን ጠቅሶ እርምጃውም በቅርቡ የፓኪስታን ወትደራዊ ኃይል ለወሰደው ጥቃት የአጸፋ እርምጃ ነው ብሏል። በሌላ በኩል የታሊባን ቃል አቀባይ የሆነው ለቢቢሲ የዜና ወኪል በሰጠው ቃል ድርጊቱ ከሙስሊም ሃይማኖት ትእዛዝ ውጭ የተደረገ የሚወገዝ ድርጊት በማለት ታሊባን እንዳልፈጸመው አስተባብሏል።

The post ፍካሬ ዜና: o ባሳለፍነው ሳምንት የግል ባንኮች ድንገተኛ የብር እጥረት ውስጥ እንደገቡ ታወቀ o ረሀቡ ህፃናትን እየፈጀ ነው o በተለያዩ አካባቢዎች ሕዝባዊ አመጽ እንደቀጠለ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

ባልተገኘበት እና ባልተካሄደ ጦርነት ተሸንፈሃል ተብሎ የተወሰነበት የአማራ ነገድ እና ኢትዮጵያዊነት

0
0

ከአበበ ተድላ

እንደምናውቀው ትህነግ (ወያኔ) ትግራይ የተባለውን ክፍለሃገር ከተቆጣጠረ በኃላ፤በተለይ አማራውን መስዋእትነት አስከፍሎ፤ ወደሌላ የኢትዮጵያ ክፍለሃገሮች ተሻግራ፤ ደርግን ከ 25 አመት በፊት ገደማ ማሸነፏ ይታወሳል። እውነቱ፤ ደርግ ማለት ትግሬን ጨምሮ የተለያዩ የኢትዮጵያ ነገዶች የተሳተፉበት ሰው በላ አምባገነን ወታደሮች መንግስት ነበረ። ነገር ግን፤በምን ስሌት እንደሆነ ባይታወቅም፤ ደርግን ሲላቸው የአማራ መንግስት በማለት አማራን አሸንፍን ሲሉ ይሰማል፤ እንዲያ ሲላቸው ደግሞ አንድ ትውልድን ያጠፋ የኢትዮጵያ ጠላትን ደርግን ስላሸነፉ ብቻ፤ ኢትዮጵያዊነትን አሸነፍን ይላሉ። እስከምናውቀው፤ ደርግ የአማራን ትውልድ፤ አድሃሪ እና ሌላ ሌላ ስም እየሰጠ ከጨረሱት መካከል ነው፤ምንም እንኳን የትህነግን ያህል አማራን ባያጠፋም። ጎንደር እኮ እንዲህ ነው ያለው ለደርግ ባለስልጣን፦

መላኩ ተፈራ የእግዜር ታናሽ ወንድም፤

ያሁኑን ማርልኝ ሁለተኛ አልወልድም። 

ታዲያ እንዴት ነው ደርግ የአማራ መንግስት ነበር የሚባለው?

በከተማዎችም ደርግ ከማንም በላይ አማራውን ነው የጨረሰው። መሪው መንግስቱም ቢሆን በአባቱ ኦሮሞ ነው። ይሄ ሁሉ እውነት ሆኖ ሳለ፤ ደርግ አማራን እንደሚወክል አድርገው፤ ደርግን ከአማራ ጋር ሆነው ካሸነፉ በኃላ፤ አማራን እንዳሸነፉት አድርገው፤ ስንት የስድብ ቃላት እና ጥቃት አማራው ላይ ሲወርድ አይተናል። ችግሩ፤ አማራው ሳይደራጅ ስለሆነ ከትህነግ ጋር ሆኖ ደርግን ለመጣል ደሙን ያፈሰሰው፤ ውጤቱ መገደል እና ምንም እንዳላደረገ መሰደብ ነው የሆነው። ይሄ የአማራው ሳይደራጅ ህይወቱን መስጠቱ ጥፋት መሆኑን ነው የሚያሳየው እንጂ፤ እነታምራት ላይኔ ደርግን ለመጣል ስንት የአማራን ልጅ ደም እንዳስፈሰሱ ይታወቃል።

amhara

ይሄ ብቻ አይደለም። አንዳንዴም የደርግን መሸነፍ የኢትዮጵያዊነት መሸነፍ አድርገው ይቆጥራሉ ትህነጎች እና አጋሮቻቸው። ልብ በሉ ደርግ አንድ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ያሰባሰበ አምባገነን መንግስት ቢሆንም፤ ሌሎች ደርግን የሚቃወሙ ነገር ግን በኢትዮጵያዊነት የሚያምኑ በርካታ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ነበሩ አሁንም አሉ። ትህነግ (ወያኔ) በምእራባዊያን እርዳታ በጦርነት ያሸነፈችው፤ስልጣን ላይ የነበረውን ደርግን ብቻ ሆኖ ሳለ፤ልክ ኢትዮጵያዊነትን እንዳሸነፉ አድርገው ነው የሚደሰኩሩት። ለዚህም ፕሮፓጋንዳ ተባባሪዎቻቸው ደሞ እነ ኦነግና ሌሎች ነፃ አውጪ ግንባር ነን ተብዬዎች ናቸው። የረሱት፤ከኢትዮጵያዊነት ሃሳብ አራማጆች መካከል ተሳስቶ ኢትዮጵያን ወደጥፋት የገፋውን የወታደሮች ስብስብ ደርግን አሸነፉ ማለት፤ ኢትዮጵያዊነትን አሸነፉ ማለት፤ እንዳልሆነ አለመገንዘባቸው ነው።

ይሄንን ከላይ ደርግን ስላሸነፉ ብቻ አማራን እና ኢትዮጵያዊነትን እንዳሸነፉ ያስባሉ ያልኩበት ምክንያት መረዳት ከፈለጋቹ፤ ይሄ አሁን ህገመንግስት ተብዬውን ህገ አራዊት ሲያፀድቁ የተገኙት ነፃ አውጪ ግንባር ተብዬዎች ብቻ እና አማራን ሳይጨምር በሺ የሚቆጠር አባላት ያላቸው ትንንሽ ሌሎች ብሄሮች ተወካዮችን ጨምሮ ሲሆን፤ በዚህ ኢትዮጵያ ላይ “ህገ መንግስት” በሚል ሽፋን የተላለፈው “የሞት ውሳኔ” ስብሰባ ላይ አንድም አማራ እና አንድም በኢትዮጵያዊነት አምናለው የሚል ድርጅት እንዳላሳተፉ ልብ ማለት ነው። አንድ ለእናቱ ፕ/ር አስራት ወልደየስ በዛ የኢትዮጵያ የጥፋት ስብሰባ ላይ ተጋብዘው ነበር። እሳቸው ይሄ ሸፍጥ ገብቷቸው መቃወማቸውን እናውቃለን። ነገር ግን ብዙ አጋር ባለማግኘታቸው ህይወታቸውን አሳጣቸው ነፍስ ይማር ብለናል። ይህ የሚያሳየው ምንም እንኳን ትህነጎች ደርግን ቢሆንም ያሸነፉት፤ አማራ ስላልተደራጀና ስላልተናገረ ብቻ አሸንፈንዋል ቀብረንዋል እንዳይነሳ አድርገን አከርካሪውን ሰብረንዋል በማለት በሃገሪቱ በተደረጉ በማንኛውም ውሳኔዎች ላይ እንዳይገኝ አደረጉት። አማራን ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያዊነት የሚያምኑትን ድርጅቶችን ጭምር ኢትዮጵያዊነትን አሸንፈናል ስላሉ እንዳይገኙ አደረጉ የነሱ አሽከር በወቅቱ ኢህዴን የሚባለውን ካልጠራቹ በስተቀር። ግን መቼ ነው አማራውን ጦርነት ገጥመው ያሸነፉት? አማራው ኢትዮጵያዊነት በሚለው ስሜት የበለጠ ስለሚያምን (ምናልባት የመንግስት ቓንቓ አማርኛ መሆኑ ጠቅሞታል ካላላቹ በስተቀር አማራ ከኢትዮጵያዊነት ከሌሎች የተለየ ምንም የተጠቀመው ነገር ባይኖርም) አማራነቱን የተለየ ቦታ ሳይሰጥ በአማራነቱ ስላልተደራጀ እና ራሱን ለማዳን ሳይደራጅ በመቅረቱ ሳይዋጉት አሸነፍነው ብለው ትህነጎች ደመደሙ። ይሄ አማራውን አንገቱን ለማስደፋት ሆን ተብሎ የሚደረግ የስነ አእምሮ ጦርነት እንደሆነ እንዳትዘነጉ። ደርግ፤ ከሁሉም ኢትዮጵያዊ የተውጣጣ ትግሬንም ጭምር የሚያካትት ሆኖ ሳለ፤ እንዲሁም ደርግ ራሱ ዋና አማራን ያጠፋ ሆኖ ሳለ (የትህነግን ያህል የከፋ ባይሆንም)፤ ደርግን ስላሸነፉ ብቻ አማራን አሸነፍነው ማለት፤ ምንም ሚዛን የማይደፋ ሃሳብ ነው። ነገር ግን እንዲህ የሚሉት እውነቱ ጠፍቷቸው ሳይሆን፤ አማራ አሁንም በአማራነት ስላልተደራጀ፤ ሳይነቃ ሆን ተብሎ አማራን አንገቱን ለማስደፋት የሚደረግ ተንኮል ነው።

ደርግን ማሸነፍ በራሱ ብቻ ኢትዮጵያዊነትን ማሸነፍ እንዳልሆነ ትህነጎች መረዳት የሚችሉት በተከታታይ በኢትዮጵያዊነት በሚያምኑ ወገኖች አሁንም ድረስ በሚነሳባቸው አመፆች ነው። ለዚህም ይመስለኛል 1997 ኢትዮጵያዊነት ሞቷል ከዚህ በኃላ ህዝቡ እኛ ባሰመርንለት አፓርታይድ ክልል ብቻ ነው የሚያስበው ብለው የልብ ልብ ተሰምቷቸው ምርጫ ገብተው ኩም ሲደረጉ፤ አሻፈረኝ ብለው ስልጣን አንለቅም ብለው የስንት ደሃ ንፁህ ደም አፍስሰው እስካሁን ስልጣን ላይ ቆዩ። አሁንም ድረስ በኢትዮጵያዊነት የሚያስቡትን እነ እስክንድር ነጋ፤ እነ አንዱአለም አራጌ ወዘተ ላይ ከሌሎቹ የብሄርተኛ ድርጅቶች ተቃዋሚዎች በላይ የከፋ ቅጣት እንዳስተላለፉባቸው አይተናል፤ አማራነታቸው የበለጠ ቅጣታቸውንም መጨመሩ እንዳለ ሆኖ።

የሚያሳዝነው ግን፤ አሁንም ኢትዮጵያዊ ነን ብለው የተደራጁት፤ የአማራን በደል፤ ያውም አማራን ነው የምትወክሉ እየተባሉ እየተብጠለጠሉ ጭምር፤ ገሸሽ ማድረጋቸው ነው። ግን አማራው ራሱን ነው እንጂ ማዳን ያለበት ሌሎች ተደራጅተው እንዲያድኑት ሊጠብቅ አይገባም። እያደረገውም ነው መደራጀቱ ተጀምርዋል፤ይቀጥላል። የበፊቱ ይቅርና አሁን ስላለው እስቲ ላውራ። እስቲ የትኛው በአንድነት ስም የተደራጀ የፖለቲካ ድርጅት ወይንም ሚዲያዎቻቸው ናቸው አማራን ከትግሬ ጋር አብሮ ኦሮሞን እና ሌላውን ኢትዮጵያዊ እየበደለ ነው ብለው ቢቢሲ እና አውሮፓ ህብረት ዜና እና መግለጫ ሲያወጡ፤ ድምፁን ከፍ አድርጎ ተዉ አማራ ተበዳይ ሆኖ ሳለ፤ የዘር ማጥፋት እየደረሰበት ሳለ ፤መልሳቹ በዳይ አትበሉት ያለው። ቢቢሲም፤ አውሮፓ ህብረትም ትህነግን ማውገዛቸው እሰየው የሚያሰኝ ነው። ነገር ግን አማራን ያለሃጢያቱ መወንጀላቸው የሚያሳዝንም ፤የሚያስጠይቅም ነው። ሲጀመር በብሄር ፖለቲካ አናምንም የምትሉ ለትህነግ ጥፋት ትግሬ ሁሉ መጠየቅ የለበትም ትላላቹ ብዬ ነበረ እኔም አምናለው ለትህነግ ጥፋት ሁሉም ትግሬ መጠየቅ የለበትም፤ ምንም እንኳን ከጥቂት ትግሬዎች በስተቀር፤ ትህነግን እና ትግሬ አንድ አድርጋቹ አትዩ ሲሉ ባይሰሙም። ይሄ አልበቃ ብሎ ምንም አማራ ስልጣን ላይ ሳይኖር (አሻንጉሊቶቹ ብአዴን ዋና ዋና መሪዎች እንኳን አማራ እንዳልሆኑ እናውቃለን)፤ አማራ ተበዳይ ሆኖ መድረሻ አጥቶ እየተንከራተተ አብሮ ከትግሬ ጋር ሲወነጀል ዝም ያሉ በተይ የአንድነት ሃይል ነን የሚሉ ብዙ አስተዛዝቦናል። እነ ኢሳትም ያቺን አማራን ያለሃጢያቱ ከትህነግ (ትግሬ) ጋር የምትወነጅለውን አረፍተ ነገር ያላነበቡ ይመስል ሌላውን የትህነግን መወገዝ ብቻ አስተጋብተው ዝም ማለታቸውም ውስጣችንን አሳዝንዋል።

የሚያሳዝነው አማራው ባልተገኘበት ውጊያ ተሸንፈሃል ተብሎ፤ በሌለበት የተከለለውን የአፓርታይድ አከላለል፤ በብሄር የተደራጁትም ሆኑ በኢትዮጵያዊነት የተደራጁት ፤ካልተቀበልክ ከአማራ ጋር አንደራደርም ይሉታል፤ አልፎ ተርፎም የድሮ ስርአት ናፋቂ ይሉታል፤ አማራው ከድሮ ስርአት የተጠቀመ ይመስል። እንግዲህ ከዚህ በላይ ምን ሞት አለ? አማራው ሳትሞት ሞተሃል መባሉ አልበቃ ብሎ እና ሁሉም የአፓርታይዱን ድንበር ለማስመር ድርሻውን ወስዶ የተረፈውን የአማራ ተብሎ የተሰጠው አልበቃ ብሎ፤ ኧረ አለው አልሞትኩም ቢልም፤ የለም ሞተሃል ብለናል ሞተሃል፤ እና በቃ የተሰጠህን የመቃብር ቦታ ብቻ ተቀበል፤ ከመባል በላይ ምን ሞት አለ! ደስ የሚለው አማራው እየነቃ ነው። እንዲህ ሸፍጥ ያቀዱለት ካሁን በኃላ በፈለጉት አይነዱትም። በአማራ ደም የምትሰራ ኢትዮጵያም ይሁን እነሱ የሚያስቡት ትንንሽ ሃገሮች አይኖሩም። ወይ አብረን በሰላም እንኖራለን ወይ ስንጠፋፋ እንኖራለን!

ኢትዮጵያዊነትም  ይኖራል ይለመልማል ነገር ግን ይቺ በአማራ ደም ሁሌ እንደአዲስ የምትሰራውን ኢትዮጵያን  ለመስራት የሚደረገው ጥረት የትም አያደርስም። አማራንም ጨምሮ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የምትሆን አገር እንዲኖረን እንስራ እንጂ ያለ አማራ ወይንም ያለ ኦሮሞ ወይንም ያለ ትግሬ ወይንም ያለ ሌላ ነገድ ኢትዮጵያ በ2 እግሮቿ አትቆምም።

በነገድ ፖለቲካ የሚያምኑትም (ምሳሌ ትህነግ፤ኦነግ/ኦህዴድ፤ኦብነግ ወዘተ)አማራውን ጠላቴ ብለው ሃገር አሳጥተው ለማጥፋት የሚያደርጉትን ከቀጠሉ፤ እንዲሁም በአንድነት ስም ያሉትም አማራውን አብሮ ከሌላው ጋር ተባብረው ለማጥፋት እና አንገቱን ለማስጎንበስ የሚያደርጉትን ጥረት ካላቆሙ አማራው ራሱን ለማዳን ይገደዳል። ይሄ ደሞ ወደ እርስ በእርስ ጦርነት የሚያመራ እንደሆነ እናምናለን ፤ግን አማራው ብቻውን ከሚያልቅ አብሮ ቢያልቅ ይሻለዋል። አማራው ደሞ ህይወትና ሞት ትርጉም ካጣለት ቆይትዋልና ሌላው ከሰላም ይልቅ በእርስ በእርስ ጦርነት ካመነ ምን እስካፍንጫቸው ቢታጠቁ ማን እንደሚጎዳ እናያለን።

ባልተሳተፍንበት ጦርነት አማራን አሸንፈንዋል አትበሉት ትህነግ እና ወዳጆቹ። አውሎንፋሱ እስኪያልፍ ብሎ አንገቱን እንደሰንበሌጥ ደፋ እንጂ ፤ነፋሱን አሳልፎ እንደገና አንገቱን ቀና ያደርጋል። አማራ አለ አልሞተም፤ አልተቀበረም ፤አከርካሪውም አልተመታም፤ አልተሸነፈም። ትህነግ ሆይ ያሸነፍሽው ደርግን ብቻ ነው ያውም የአማራ ደም ፈሶ ጭምር።

ኢትዮጵያዊነትም አልሞተም ምንም እንኳን በኢትዮጵያዊነት ስም ያሉ ቢያጭበረብሩበትም በአማራ ደም ኢትዮጵያን ሊያቆሙ ቢሞክሩም፤ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ እኩል የምታደርግ ኢትዮጵያዊነት አሁንም አልሞተችም አለች።

ፉከራ አይደለም ለውጥ እያየን ነው፤እውነት ነው አማራው ይነሳል፤ አልተሸነፈም፤አልሞተም፤ እንዳላቹት አልተቀበረም!!! ሁሉንም እኩል የምታደርግ ኢትዮጵያም አለች አልሞተችም!!!

የአማራ ልጅ ተደራጅቶ ራሱንም የአባት የእናቶቹን ሃገርም ያድናል!!!

ጥር 2008

The post ባልተገኘበት እና ባልተካሄደ ጦርነት ተሸንፈሃል ተብሎ የተወሰነበት የአማራ ነገድ እና ኢትዮጵያዊነት appeared first on Zehabesha Amharic.

የቡዳ ፖለቲካና የአቶ ግርማ ሰይፉ እይታ

0
0

Merera gudina dr

አቶ ግርማ ሰይፉ ለዶ/ር መራራ “የቡዳ ፖለቲካ እና መቀበል ያቃተው መራራ እውነት” በሚል ርዕስ  የተፃፈውን አነበብኩ፡፡ የዶ/ር መራራን “የኢትዮጲያ ታሪክ ፈተናዎችና የሚጋጩ ህልሞች” የሚለውን መጽሐፍ ባላነብም ዶ/ር መራራ እንደጸበል መድሀኒት የሚያዙትን የአማራና የኦሮሞ ልሂቃን   ወደመሀል የመምጣት ፖለቲካውን ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ስለምከታተለው አዲሱ መፅሐፉቸውም የፀበሉ አካል እንደሚሆን እገምታለሁ፡፡ ከሀገር ቤታችን በተለያዩ ምክንያቶች ወጥተን   ፈቅደንም ሆነ ሳንፈቅድ የኢትዮጲያ ፖለቲካ አካል ለሆንን ወገኖች ግርምት የሚፈጥሩ በርካታ ሁኔታዎችን እየተመለከትን ነው፡፡

አቶ ግርማ ሰይፉ ከማክብራቸው አንድነት ፖርቲ አመራር አባል አንዱ ነበሩ፡፡ ዶ/ር መራራ ለረዥም አመታት ( ኦብኮ) መሪነታቸው በኢትዮጲያ ፖለቲካ ውስጥ ባላቸው ተሳተፎ አውቃቸዋለሁ፡፡ በሁለቱ መካከል የዕድሜ ልዩነት ብቻ ሳይሆን ከዘመኑ ጋር የሚፈጠር የአስተሳሰብ ሁለንተናዊ አመለካከት ልዩነት ቢኖርም በፖለቲካው ግን አንድ ያደርጋቸዋል ብዬ የማስበው ሁለቱም በኢትዮጲያዊነታቸውና በኢትዮጲያ ፍትህ እኩልነት ሰላም እንዲሰፍን ያላቸው አቋም ጥያቄ ውስጥ የሚገባ አይደለም፡፡ ምንም እንኳን በሐሜት ደረጃ አዳንዶች ዶ/ር መራራ በብሔረሰብ ድርጅት ስለታቀፉ ወይም ስላቋቋሙ ከኢትዮጲያዊነታቸው ላይ ትንሽ ሸረፍ ለማድረግ ሲሞክሩ ቢታዩም የአቶ ግርማንም በሥርዓቱ ላይ ጠንካራ አቋም የሌላቸው አድርገው የሚሥሉ የፖለቲካ ሰዓሊዎች ባይጠፉም ሁለቱም       ለትግሉ ያበረከቱት አስተዋፅኦ እጅግ የላቀ ነው፡፡ ዛሬ ሀጊሪቱ ካላት ፖለቲከኞች ውስጥ በአንጋፋነት የመሚደቡ ናቸው፡፡ ይህን በመጠኑ ካልኩ በኋላ ሰሙኑን አቶ ግርማ የዶ/ር መራራ የቡዳ ፖለቲካ በመተቸት የጻፉትና እግረ መንገዳቸውንም በአነድነትና በመድረክ የተፈጠረውን ውዝግብ ሂደት ለማሳየት የሞከሩበትን የዘገየም ቢሆን ብዙ ኢትዮጲያውያንን ተስፋ ያስቆረጠ ፍችን ከድርጅታዊ ስሜት ውጭ ላለነው ወገኖች የተሰጠው አስተያየት በመጠኑም ቢሆን ሳያስገርመን አልቀረም::

በመጀመሪያ ወንድሜ አቶ ግርማ ዶ/ር መራራ ዛሬም የመኤሶን አስተሳሰብ ያላቸው ናቸው በ  ማለት ኮንነዋቸዋል ::  ለፕሮፈሰር መራራ ለመናገር ሳይሆን  ለኩነኔ ው ግን ማረጋገጫ አልሰጡም በፖለቲካ አሳማኘ የሆኑ ነጥቦችን በማንሳት አቶ ግርማን የማውቃቸው ቢሆንም   እንደ እኔ ግምት ትላንት ግለሰቦች የነበሩበትን የፖለቲካ ድርጅት ስም በመጥራት ኢህአፓ መኤሶን ደርግ ኢሰፓ  ትመስላለህ በማለት ትላንት የተከፈለውን መስዋዕትነት በማሸማቀቂያ ፖለቲካ ለማቅረብ መሞከር ተገቢ አይመስለኝም፡፡ ዋናው ፍሬ ነገር ብዙ ኢትዮጲያውያን ተስፋ ጥለንበት የነበው አንድነትና  ቀረው መድረክ እንዴት  ሊለያይ  ቻለ የሚለው ጥያቄ በውጭ የምንገኘው ኢትዮጲያውያን የመድረክ ደጋፊዎችም የምናውቀውን ያህል ማለት ተገቢ ይመስለናል፡፡  በመጀመሪያ በግሌ መድረክን ለመደገፍ ያነሳሳኝ የመድረክ ማኒፌስቶ    ሁሉን አሳታፊና በተለያዩ የሀገራችን ፖለቲካ እምብርት  የሆነውን

ጥያቄዎች  ማለትም

የብሄረሰብ ችግሮችን አፈታት

የሉአላዊነት ጥያቄና

የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ላይ  ያላቸው የጋራ አመለካከትና ይህንኑም ለመፍታት

ከጠረጴዛ ዙሪያ ውጪ ምንም መፍተሔ የሌለው በውይይትና በሂደት ሰጥቶ በመቀበል ፖለቲካ ሁሉም አንድነት ፖርቲን እንዲመስሉ ሳይሆን በልዩነት አንድነትን ሊያመጡ የሚችሉ ስብስቦች ናቸው ከሚል ቅን እምነት ነው::  ከዚህም ባሻገር አምባገነኑን ስርዓት ለመጣል ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል አካል የሆነውን ብሔራዊ መግባባትን እንደ አንድ የመፍትሄ ሃሳብ  አጀንዳው አድርጎ መነሳቱ ነው፡፡ በእርግጥም በተለያዩ ጉዳች ላይ የወሰዷቸው የጋራ አቋሞች ወደዚያ ሂደት የመሩ እንደነበር  ግልጽ ነው::

በዲያስፖራ የምንገኝ በርካታ ኢትዮጲያውያን ይሄን ጅምር ለማበረታታት ያለምንም አደራጅነት ነፃ በሆነ መድረክን ለመደገፍ በራሳችን መሰባሰብ ነበረብን፡፡ በርግጥ በወቅቱ በዲያስፖራው የአንድነት ደጋፊዎች ቁጥር በርካታ ሲሆኑ ቀጥሎ አረና ትግራይ የተሻለ ደጋፊ ያሰው ኃይል የነበረው ነው፡፡ ኦብኮም በየአካባቢው ትንሽ ደጋፎዎች ያሉት ሲሆን በዶ/ር በየነ የሚመራው ድርጅት በቁጥር አነስተኛ ደጋፊ እንዳለው የድርጅቶቹን  ጩኸት በመጮህ የፖለቲካ ስራ በመስራት ሊመዘን እንደሚችል ግልጽ ነው፡፡ ከሚዲያዎች የሚዲያ ባለቤቶቹ የመድረክ አባል ድርጅቶች አባል ወይም ደጋፊ የሆኑ ግለሰቦች ከፖለቲከኞችም እንደዚሁ ለመድረክ የጋራ ጩኸትን በማሰማት ትልቅ ድጋፍ እንደነበረው ግልጽ ነው፡፡  ወደ ውህደት እንዲሸጋገሩ በዲያስፖራው በኩልም ትልቅ  ግፊት ነበር፡፡ እንዲያውም ለአባል ድርጅቶቹ በግልም ሆነ በጋራ በዲያስፖራው አንድ ወጥ የሆነ የመድረክ ድጋፍ ኮሚቴ እንዲቋቋም ይህም ጊዜን ጉልበትን እውቀትን ለማስተባበር እንደሚረዳ ጥያቄ ቀርቦ ነበር፡፡ በተለይም ዲያስፖራው ትልቅ ድጋፍ በፋይናስ ስለሆነ ለየድርጅቶቹ የተበጣጠሰ ድጋፍ ከማድረግ እንደሚያድን የታመነ ስለነበር ነው ::በመድረክ አብል ድርጅቶችና በአንድነት መካከል የነበረው ሽኩቻ ውስጥ ውስጡን ሲብላላ ቆይቶ ዶ/ር መራራና አቶ ግርማ ሰይፉ ወደውጭ በወጡበት ወቅት ያልተጠበቀ ክስተት ተፈጠረ :: ደጋፊዎችን በጋራ ከማወያየትና ስብሰባ ከማድረግ ይልቅ እነ መራራ አላሰሩንም ከነሱ ጋር መጎተት አንችልም የሚሉ የአንድነት ደጋፊዎች ጩኸትና አንድነቶች ገንዘብ ስላላቸው ሊጫኑን ይፈልጋሉ የሚለው የሌሎቹ መድረክ አባል ድርጅቶችችበየፊስቡኩና በየዌብ ሳይቱ መታየት ጀመረ እጅግ የሚገርመው ብዙዎቻችን የማንም ድርጅት አባል ሳንሆን መድረክ ይጠናከራል በሚልና የአንዱ ወደኋላ መቅረት ሌላውንም እንዳያዳክም ለአንድነት ለኦብኮም  ለአረናም   የሚውል የገንዘብ ድጋፍ

በተጠየቅን ጊዜ እናደርግ እንደነበረ ነው፡፡ በኋላ ላይ የአንድነት ደጋፊዎች ነን ከሚሉት ውስጥ አንድነትን ከመድረክ በማስወጣት  በወቀቱ  የፓለቲካ ጫጉላውን ያከብር በነበረው ሰማያዊ ፓርቲ ጋር እንዲዋሃድ ጩኸታቸውን ማሰማት ጀመሩ::

መድረክም ረዥም ጉዞ ተጉዞ ወደተሸለ ደረጃ መምጣት ሲገባውም ጠንካራ ሀይሉ የሆነውን አንድነትን አግጄዋለሁ የሚል መግለጫ አወጣ፡፡ ምንም እንኳን አንድነት ከመድረክ የተለየበት መሠረታዊ የልዩነት ነጥቦች የሉም ባይባልም ትልቁ ምክንያት ግን የአንድት   ደጋፊዎች    አንድነትን ለመምጣት ሁሉም የአንድነት ፓርቲን እንዲመስል   የፈለጉበት ጊዜውን ያልጠበቀና በብሔረሰብ የተደራጁትም የአቅም ማነስ ጉዳይ ወደብሔረሰብ ጉያ እንዲሸጎጡ መሆኑ ነው፡፡  ከድርጅቱ ፕሮግራም ይልቅ አንድነት የሚለው ቃል የሚያሰባሰባቸው በርካታ ኢትዮጲያዊያኖች አሉ፡፡ ችግሩ ለአንዳንድ ወገኖቻችን አንድነትን የጠየቀ ሁሉ በአማራ ፖለቲካ ስብስብ ውስጥ እንዲነከሩ መፈለጉ ነው፡፡ በብሔረሰብ የተደራጁትን በኢትዮጲያዊነታቸው ላይ ጎሰኞች በሚል እንደምናቀርበው ማለት ነው፡፡ ለዚህ ነው ዶ/ር መራራም ከዚህ ፖለቲካ መጓተት ውጭ ሊሆኑ ያልቻሉትና የአማራና ኦሮሞ ኢሊት ወደመሃል መምጣት የሚለውን ፖለቲካ ለመጫወት የፈለጉት። ዛሬ በርግጥ ትልቁ ገመድ ጉተታ ያለው በአማራው በኦሮሞውና በትግሬው ሊሂቃን መካከል ነው፡፡ ይህ ደግሞ ያለምክንያት ሳይሆን ያለፉት ስርዓቶችን የአሁኑንም ጨምሮ እነዚህ ብሔረሰቦች በፖለቲካው በኢኮኖሚውና በትምህርተ ዘርፍ ጭምር ከሰጣቸው ቦታ የሚመነጭ ነው፡፡ የአማራው የኦሮሞና ወይም የትግሬ ሊሂቃን በኢትዮጲያ ውስጥ የሚኖራቸው የፖለቲካ ተሳትፎና  እንደፈለገ ሕብረተሰቡን ማሽከርከር የሚያቆመው ከአማራነት ከኦሮሞነት  ከትግሬነት ወዘተ   በአጠቃላይም በብሔረሰብ ማሰብ አቁመን  እድገት ብልጽግና ፍትህ ሰላም እኩልነትን ለሰው ልጅ ይገባዋል ከሚል እምነት ስንነሳ ነው፡፡  ማለፍ የማንችለውን የታሪክ ሀቅ ጋር መታገል ሳይሆን በፖለቲካ ጥበብ  ነባራዊ ሁኔታውን ወደ ተሻለ አቅጣጫ እንዲጉዋዝ መግፋት ነው።ዛሬ  በርካታ ኢትዮጵያውያንና የፖለቲካ ድርጅቶችም ጭምር በጋራ መስራትን መተባበርን አስፈላጊነት ጠዋትና ማታ የማይሰብኩበት ጊዜ የለም። የሚያሳዝነው ግን ለርዥም ጊዜ ታላቅ መስዋእትነት ተከፍሎበት የተሰራውን ህብረት በጥቂት ቀናት ውስጥ እያፈረስን ሌላ መገንባት ባህል እየሆነ መምጣቱ ነው። የፖለቲካ ምሁሮቻችንም የሃይል አሰላለፍ አቅዋም በየሳምንቱ እየተቀያየረ መሰረታዊ መርሆዋችን ጭምር በፖለቲካ ታክቲክ እየደፈጠጥን አንዱንም ሳንሆን እየዋዥቅን እንገኛለን ። በብሄረሰብ ወይም በጎሳ ተደራጅቶ የኢትዮጵያን ችግር መፍታት እንደማይቻል ካለፉት ልምዶቻችን በሚገባ የተማርን ቢሆንም ከህብረተሰባችን እድገት ማለትም ዛሬም የብሄረሰብ ፖለቲካን የሚሸክም ህብረተሰብ ቁጥር ቀላል አለመሆኑን መረዳቱና ተመጣጣኝ የፖለቲካ ስትራተጂና ታክቲክ መንደፉ ሊታለፍ የሚገባው ጉዳይ አይደለም። የብሄረሰብ ፖለቲካ ድርጅቶች የሚያንቀሳቅሱትን የፖለቲካ መስመርና ጥያቄ እየደገፍንና አብርናችሁ እንሞታለን እያለን እየፎከርን በሌላ በኩል ለምን በብሄረሰብ ተደራጁ እያልን የተሰበሰበውን መበተን መፍትሄ ሊሆን አይችልም። መድረክ በዚህ ረገድ የጀመረው ጉዞ ባይቀጭ ኑሮ ዛረ አምባገነኑን ስራት በጋራ ቆመን በታገልነው ነበር።   መድረክን የደገፍንበት ትልቁ አላማም በሂደት በመነጋገር መመወያየት በመተማመን አብሮ መስዋእትነት በመክፈል የተፈለገውን ሃገራዊ አጀንዳ ወደአለው የፖለቲካ ድርጅት ይቀየራል በሚል እምነት ነበር:: ዛረም በዚህ ሂደት ላይ ያሉና በጋራ ለመስራት የተዘጋጁ የፖለቲካ ድርጅቶች ሊያልፉት የማይችሉት የሃገራችን ነባራዊ ሁኔታ ነው። በተለይም በሃገር ቤት ያሉና በሰላማዊ መንገድ ትግሉን የተያያዙት ድርጅቶች እየወደቁም እየተነሱም መሪዎቻቸውና ደጋፊዎቻቸውንም ሂይወት በመስዋእትነት እየገበሩም ህዝቡን ከጊዜ ወደጊዜ ለአምባገነኖች ምቹ ፍራሽ እንዳልሆነላቸው እይተመለከትን ነው። ይህ በቀላሉ የተገኘ ሳይሆን ህዝብን ከማንቃት ከማደራጀት በጋራ ከማታገል የሚመነጭ የታሪክ እውነት ሂደት ነው። ህዝቡ የጎደለው አንድ ነገር ነው በአንድነት ስም ወይም በብሄረሰብ ስም የመደራጀትና ያለመደራጀት ሳይሆን የጠራ የፖለቲካ ግብ ያለውና የሃገሪቱን አንድነት የህዝቦችን እኩልነት የዲሞክራሲና የፍትህ ስራትን ለመመስረት የሚችል በራሱ ድርጅታዊ ህይዎት አርአያ የሆነ የፖለቲካ ሃይል ነው። ከሁሉም በላይ የሃገሪቱን ችግሮች ለመፍታት ሆደ ሰፊና ከሽፍጥ የጸዳ የፖለቲካ አሰላለፍ ነው። ሲሞቅ ብሄርተኛ ሲቀዘቅዝ ጎሰኛ በቲዮሪ አንድነትን ሰባኪ በተግባር አንድነትን ሸርሻሪ የሰላማዊ ትግሉ  ሲያይል ሰላማዊ   የጦርነት አታሞ ሲመታ አካኪ ዘራፍ ባይ በሞላበት የፖለቲካ ጉዞ አትራፊው በስልጣን ላይ ያለውና ሃገሪቱን በአጥንትዋ እያስቀረ ያለው የጥቂት ፋሽስታዊ መንገድ አራማጆችና ጸረ ኢትዮጵያ አቅዋም ያላቸው ጠላቶቻችን ናቸው። ባለፈው የፖለቲካ ድርጅቶች የእርስ በርስ መናቆርና አልያም ጠብቀኝ ነጻ ላወጣህ ነው ከሚል ደረቅ ፕሮፓጋንዳ ተላቀን አንድ እርምጃ ወደፊት መራመድን ይጠይቃል ::

ወንድሜ አቶ ግርማ ሰዪፉ ከአንድነት መፍረስ በሁዋላ  ህዝቡ የዚህ አይነት የፖለቲካ ድርጅት እንደሚያስፈልገው የጠቆሙበት ጊዘ እንዳለ አስታውሳለሁ። በየትም ይምጣ በየትም በታሪክ አጋጣሚና በሃገራችን ነባራዊ ሁኔታ ላይ የተፈጠሩትን የብሄረሰብ የፖለቲካ ድርጅቶችን የሚያገል ወይም የአንድነት የፖለቲካ ድርጅቶችን የሚያቀጭጭ የፖለቲካ ስብስብ አሁን ተነስተን በአንዴ ልንገነባው የምንችልበት ሁኔታ ግን ያለ አይመስለኘም። መፍትሄው የመድረክን ሰጥቶ የመቀበልና ብሄራዊ መግባባትን ያማከለ አስተሳሰብ በሂደትም የማይፈለገውን አስተሳሰብ የሚያስወግድ እስትራተጂ ሊቀየስ ይገባል።

gishag70@yahoo.com

The post የቡዳ ፖለቲካና የአቶ ግርማ ሰይፉ እይታ appeared first on Zehabesha Amharic.

Ethiopia’s First Woman Professor Yalemtsehay Mekonen Won 2015 African Union Kwame Nkrumah

0
0
YalemtsehayMekonnen-

YalemtsehayMekonnen-

Ethiopian Prof. Yalemtsehay Mekonnen has won the 2015 African Union Kwame Nkrumah

Scientific Awards for her scientific achievement and valuable discoveries and findings that have contributed to the development agenda of the Continent.

Prof. Merzouk Hafida from Algeria also received the award representing the Northregion.

The award ceremony took place on 20 January 2016 during the closing of the 8th African Union Gender Pre-Summit.

The prestigious African Union Kwame Nkrumah Scientific Awards programme was launched on 9 September 2008, with the objective to give out scientific awards to top African scientists particularly the women.

The two female laureates of the AU Kwame Nkrumah Scientific Awards received a cheque of 20,000 USD each, a gold plate medal, a certificate and flowers from the representatives of the AU Commission.

Prof. Yalemtsehay joined the Addis Ababa University (AAU) in 1972 obtaining her B. Sc degree in Biology in 1977. She was then employed as a graduate assistant in the Department of Biology, Faculty of Science where she joined the first graduate programme launched in the Department.

She received her M.Sc degree in Zoology in 1980 with the first batch of graduates as the first woman both at the AAU and the country. She obtained her PhD in Human Physiology from the University of Heidelberg Germany in May 1992. She was promoted to the rank of full professor in January 2009.

She was awarded with several research grants and fellowships nationally and internationally. To give some examples, the Ethiopian Science and Technology Commission, the Ethiopian Agricultural Research Organization, the British Council, the International Foundation for Science, the Third World Academy of Sciences, the German Academic Exchange Service and the Alexander von Humboldt Foundation, Germany.

Her main scientific work focuses on medicinal plants that are used by communities and test them in the laboratory if they have medicinal importance and assessing health hazard to humans, animals and the environment due to chemicals and other contaminants that are by-products of agricultural practices or industries.

She has collaborated with researchers in Ethiopia and abroad and advised many graduate students. The outcome of her research work is exemplified by 92 publications in national and international peer reviewed scientific journals.

Currently she is engaged in teaching and continuing her research activities in the College of Natural Sciences, AAU. In addition she is engaged in several professional activities (E.g. Member of the New York Academy of Sciences, Board member of the Ethiopian Academy of Sciences, Executive Board President of the Society of Ethiopian Women in Science & Technology).

She has great passion to motivate the young specially women to be confident and successful in their professional career in particular and their overall walk in life in general.

Source: AU

The post Ethiopia’s First Woman Professor Yalemtsehay Mekonen Won 2015 African Union Kwame Nkrumah appeared first on Zehabesha Amharic.


‹‹ማዕከላዊ ነው እንዴ ያለነው?›› (ክፍል ፩) በናትናኤል ፈለቀ

0
0

በናትናኤል ፈለቀ
እራሳቸውን ድንገት ስተው ‹‹ኮማ›› ውስጥ የገቡ ወላጅ አባቱን ለማስታመም እና በቅርቡ ሕይወታቸው ያለፈውን አሳዳጊ ሴት አያቱን እርም ሊያወጣ ከ15 ዓመት በላይ ወደተለያት ሀገሩ እየተመለሰ ነው፡፡ ለጉዞው ቀና ብሎ ያሰበው መንገድ ከሚኖርበት ሴንት ፖውል፣ ሚኒሶታ ወደካናዳዋ ቶሮንቶ አቅንቶ ከዛ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አዲስ አበባ ለመግባት እና በማግስቱ አውቶቢስ ተሳፍሮ አባቱን ወደሚያገኝበት የሱማሌ ክልል ከተማ ጎዴ ማምራትን ነበር፡፡
ወደ ሀገሩ ተመልሶ አባቱን ለማግኘት እጅግ ቸኩሏል፤ ተጨንቋል፡፡ ጭንቀቱን የሚያሳብቀው ገና ከተወለደች ሁለት ሳምንት ያልሞላትን ሁለተኛ ልጁን እና የሦስት ዓመት ወንድ ልጁን አራስ ባለቤቱ ላይ ጥሎ ጉዞውን መጀመሩ ነው፡፡ ነገሮች ሁሉ እንዳቀደው ከሄዱለት በአንድ ወር ግዜ ውስጥ የኢትዮጵያ ቆይታውን አጠናቆ ዜጋዋ አድርጋ ወደተቀበለችው አሜሪካን ይመለሳል፡፡

Natnael-Feleke-620x330

በኢትዮጵያውያን አቆጣጠር ግንቦት 29 ቀን፣ 2006 ዓ.ም ዕለተ ዓርብ የ31 ዓመቱ ፈረሃን ኢብራሂም አዲስ አበባ ዓለም አቀፍ የጢያራ ማረፊያ ደረሰ፡፡ አብረውት አዲስ አበባ እንዲደርሱ የሸከፋቸው ሻንጣዎች ግን አልደረሱም፡፡ ጉዳዩን ያስረዳቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች ጓዙ የሚመጣው በሚቀጥለው በረራ እንደሚሆን፤ ይህ ማለት ደግሞ አዲስ አበባ የሚደርሰው ከሁለት ቀን በኋላ እንደሚሆን አስረዱት፡፡ የዕቅዱ መዛነፍ የመጀመርያ ምዕራፍ ይህ ሆነ፡፡ ነገርየው ብዙም የሚያስጨንቅ ሆኖ አላገኘውም፡፡ በሥራው ምክንያት የብዙ ግዜ የአየር ጉዞ ልምድ ስላለው እንደዚህ ዓይነት አጋጣሚዎች ሊፈጠሩ እንደሚችሉ ያውቃል፡፡ አባቱን የሚያገኝበት ግዜ መራዘሙ ቢያሳስበውም አዲስ አበባ ውስጥ ሁለት ቀን እንዲቆይ መገደዱ ከተማዋን ዞር ዞር ብሎ ለማየት የሚፈጥርለትን ዕድል በማሰብ ለመፅናናት ሞከረ፡፡
***
ፋይሰል ሜድኮ ባዮ ሜዲካል ኮሌጅ ውስጥ የሁለተኛ ዓመት የፋርማሲ ተማሪ ነው፡፡ የትምህርት ወጪውን የሚሸፍንለት በፎቶ ብቻ የሚያውቀው የአጎቱ ልጅ ከአሜሪካን ሀገር ሲመጣ ተቀብሎ አዲስ አበባ ያለውን መስተንግዶ ጨርሶ ወደጎዴ ለመላክ ያለውን ኃላፊነት እሱ ወስዷል፡፡ የአጎቱ ልጅ ሲያገኘው እንዲኮራበትም በቅርቡ በላከለት ገንዘብ ያሰፋውን ጥቁር ሱፍ ግጥም አድርጎ ለብሶ፣ አበባ ይዞ ቦሌ ዓለም አቀፍ ጢያራ ማረፊያ መንገደኞችን ለመቀበል ከተደረደሩት ሰዎች መኻከል ተገኝቷል፡፡
እሁድ ሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 12፡30 ገደማ ፋይሰል ፈጽሞ ሊገባው ባልቻለ ሁኔታ እራሱን የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ የተጠርጣሪዎች ማረፊያ ክፍል ቁጥር 9 ውስጥ አግኝቶታል፡፡ ከሱ አስቀድሞ ክፍሉ ውስጥ ነበሩትን ሰዎች ምን እየተፈጠረ እንደሆነ እንዲያስረዱት በሚችላት ትንሽ አማርኛ ተፍጨረጨረ፡፡ ሊገባው የቻለው ነገር ያለበት ቦታ በተለምዶ ማዕከላዊ እየተባለ እንደሚጠራ እና ያሉበት ክፍል የሚገኝበት ሕንፃ በቅዝቃዜው ምክንያት ‹‹ሳይቤርያ›› የሚል ስያሜ እንደተሰጠው
ብቻ ነው፡፡
***
ፈረሃን ለመጀመርያ ጊዜ በዕጁ ያጠለቀውን ካቴና ፈትተው አንድ ደብዛዛ ብርሃን ያለበት ክፍል በር ከፍተው ገፈተሩት፡፡ ከሻንጣው ውስጥ ወደማረፊያ ቤቱ ይዞት እንዲገባ የተፈቀደለትን አንድ ቅያሪ ቱታ እና የጥርስ ብሩሽ እና ሳሙና በቢጫ ፌስታል እንዳንጠለጠለ በሩ አጠገብ ቆሞ የገባበትን ክፍል ይቃኝ ጀመር፡፡ በር ድረስ አጅበው ይዘውት የመጡት ሰማያዊ ቀለም ያለው ሬንጀር የለበሱ ሰዎች በሩን ሲዘጉት የወጣው ድምጽ የክፍሉን ቅኝት አቋርጦ በድንጋጤ ከበሩ አካባቢ እንዲርቅ አስገደደው፡፡
ደቂቃዎች አለፉ፤ ፌስታሉን በዕጁ እንዳንጠለጠለ ቆሟል፡፡ ቀድመው ክፍሉ ውስጥ የነበሩትን ሰዎች ቆጠራቸው፣ 13 ነበሩ፡፡ ‹‹ቁጭ በል›› ብለው ቢጋብዙትም አልገባውም፡፡ በቋንቋ እንዳልተግባቡ ሲረዱ ከመካከላቸው ተኝቶ የነበረ አንድ ልጅ ቀሰቀሱና ‹እንግዳ ተቀበል› አሉት፡፡ ከንቅልፉ የተቀሰቀሰው ልጅ ከፍራሹ ተነስቶ ወደቆመው ሰውዬ አመራና እጁን ለሰላምታ ዘረጋ፡፡ ኡመድ ብሎ እራሱን አስተዋወቀ;; የቆመው ሰውዬ ለሰላምታ የተዘረጋለትን እጅ በቸልታ እየጨበጠ ‹‹ፈረሃን እባላለሁ›› አለ፡፡ ኡመድ ሌላኛውን እጁን ፌስታሉን ለመቀበል እየሰደደ እንግዳውን እንግሊዘኛ መናገር ይችል እንደሆነ ጠየቀ፡፡ ፈረሃን ጭንቅላቱን ላይ ታች ወዝውዞ መለሰለት፡፡ ሊግባባው ሚችል ሰው ማግኘቱ ቢያስደስተውም አሁንም ፈፅሞ ደኅንነት እየተሰማው አይደለም፡፡ ለማየት የሚረዳውን መነጽር ከዓይኑ ላይ አወረደና በእጁ ያዘ፡፡ አንድ ጊዜ እንደገና ክፍሉን ቃኘ፡፡ በኮንክሪት የተሰራ ጣራ እና ግርግዳ፣ ለአየር መውጫና መግቢያ እንዲሁም የኤሌክትሪክ ብርሃን የሚገባበት በፍርግርግ ብረት የተገደበ ከበሩ በስተግራ በኩል ጣራውን ታክኮ ያለ ትንሽ ክፍተት፣ ክፍሉ ውስጥ ባሉ ሰዎች ቁጥር ልክ የሚመስል ጥግ ይዘው የተደረደሩ የውኃ ማሸጊያ ላስቲኮች፣… ከላስቲኮቹ መኻከል አንዳንዶቹ ውስጥ ያለው ፈሳሽ ሽንት ስለመሰለው በመጠየፍ መራቅ ፈለገ፡፡ ኡመድ ተኝቶ ወደነበረበት ፍራሽ ተመለሰና ‹‹ፈረሃን፣ ወደዚህ ና›› ሲል ጋበዘው፡፡ ከላስቲኮቹ መራቅ የፈለገው ፈረሃን በትክክለኛው ሰዓት የመጣለትን ግብዣ ተቀብሎ ጫማውን አወለቀና በፍራሾች ላይ ተረማምዶ ከኡመድ አጠገብ ተቀመጠ፡፡
ክፍሉ ውስጥ ያሉት ሌሎች ሰዎች የኡመድ እና የፈረሃንን ዓይን አፈራርቀው እያዩ ለኡመድ በጥያቄ አጣደፉት፡፡ ኡመድ ወደፈረሃን ዞሮ ‹‹ሱማሌ ትመስላለህ?›› አለው፡፡ ፈረሃን በመስማማት በመስማማት ጭንቅላቱን ነቀነቀ፡፡ ኡመድ አብረውት ከታሰሩ ሶማሌዎች ካስተማሩት የሚያስታውሳትን ሱማልኛ ተናገረ ‹‹ማፊዓንታሃይ?›› ፈረሃን ክፍሉ ውስጥ ከገባ በኋላ ለመጀመሪያ ግዜ ፈገግ ብሎ መልስ ሰጠ – ‹‹ፊዓን›› ሲል፡፡ የሚችለውን ሱማልኛ የጨረሰው ኡመድ በእንግሊዘኛ መናገር ቀጠለ፡፡ ‹‹ከየት ነው የመጣኸው?›› ፈረሃን ጥያቄውን ለመመለስ ጥቂት ሰከንዶች ከወሰደ በኋላ የሚኖረው አሜሪካን ሀገር እደሆነ፣ ለጥቂት ግዜ እረፍት ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣ አስረዳ፡፡ ኡመድ ጥያቄውን ቀጥሎ ለምን እንደታሰረ ያውቅ እደሆነ ጠየቀው፡፡ ፈረሃን ግራ መጋባቱን በሚያሳብቅ ሁኔታ ዓይኑን ግራና ቀኝ ካንከባለለ በኋላ ትከሻውን ሰብቆ የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ገለፀ፡፡ አብረዋቸው ያሉት ሰዎች ጥያቄዎቻቸውን እያዥጎደጎዱ እንዲያስተረጉምላቸው ቢፈልጉም ከዚህ በላይ ፈረሃንን ማስጨነቅ ያልመረጠው ኡመድ ‹‹አሁን ተረጋግተህ እረፍት አድርግና ጠዋት እናወራለን፡፡ ለሁላችንም የሚበቃ ፍራሽ ስለሌለ ከኔ ጋር ፍራሽ እንጋራለን፡፡ ሽንት መሽናት ከፈለክ ከነዛ ላስቲኮች አንዱን ተጠቀም፡፡›› አለውና አንሶላ አነጠፈለት፡፡ ፈረሃን ‹‹አመሰግናለሁ›› አለና እንደማመንታት ብሎ ማውራት ቀጠለ፡፡ ‹‹ታውቃለህ? መጀመሪያ እዚህ ሲያስገቡኝ የምትደበድቡኝ መስሎኝ ነበር፡፡ እኔ የምኖርበት ሀገር እስር ቤት ውስጥ አዲስ ሰው ሲገባ የቆዩት እስረኞች በድብደባ ነው አቀባበል የሚያደርጉለት፡፡›› ኡመድ ጮክ ብሎ ሳቀ፡፡ ሌሎቹ እስረኞች ምን እንዳሳቀው ለማወቅ ጓግተው ጠየቁት፡፡ ፈረሃን የነገረውን ተረጎመላቸው፡፡ ሁሉም እየተሳሳቁ ፍራሾቻቸውን ማንጠፍ ጀመሩ፡፡ ኡመድ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሌሎች እስር ቤቶች ውስጥም ተመሳሳይ ነገር ሊከሰት እንደሚችል ለፈረሃን አስረዳው፡፡
ፈረሃን ለመተኛት ትንሽ ሲገላበጥ ቆየና የረሳው አንድ ነገር ድንገት ትዝ አለውና ኡመድን ‹‹ፀሎት ማድረግ እችላለሁ?›› ብሎ ጠየቀው፡፡ ኡመድ፤ በክፍሉ ውስጥ የነበሩት የእስልምና ዕምነት ተከታዮች የመግሪብ ፀሎት እንዳደረጉ፣ ትንሽ ከቆየ አብሯቸው የኢሻ ፀሎት ማድረግ እንደሚችል አልያ ግን ብቻውን ቢፀልይ ችግር እንደሌለው እና ቦታ ሊያመቻችለት እንደሚችል ነገረው፡፡ ፈረሃን ቆይቶ በጋራ ፀሎት ማድረጉን መረጠ፡፡
***
ከእንቅልፉ ነቅቶ አይኑን ሲገልጥ ግር ተሰኘ፡፡ ዙሪያውን ሲያይ የማያውቀው ቦታ እራሱን ስላገኘው ተደናገጠ፡፡ ዓይኖቹን አሻቸው፤ የተለወጠ ነገር ግን አልነበረም፡፡ ቀስ ብሎ ለማስታወስ ሞከረ፡፡ ደስ የማይል ስሜት ውስጡን ሲወረው ተሰማው፡፡ ከ17 ሰዓታት በፊት የተፈጠረውን ነገር አስታወሰ፡፡ በህልሙ ቢሆን ምርጫው ነበር፡፡
***
የዘገዩት ሻንጣዎችን ለማምጣት እሁድ ረፋድ ላይ ካረፈበት ሆቴል ታክሲ ተኮናትሮ ወደቦሌ አቀና፡፡ የአየር መንገዱ ሰራተኞች ለተፈጠረው ስህተት እና መጉላላት ይቅርታ ጠይቀው ሻንጣዎቹን አስረክበው ሸኙት፡፡ ወዳረፈበት ሆቴል እየተመለሰ ለፋይሰል የስልክ ጥሪ አደረገና የዘገዩት ሻንጣዎች በእጁ መግባታቸውን ከነገረው በኋላ ወደጎዴ የሚወስደውን የአውቶቢስ ትኬት ለመቁረጥ ሰኞ ጠዋት ለመገናኘት ተቀጣጠሩ፡፡ ፋይሰል ያረፈበት ሆቴል ድረስ መጥቶ አብረው ሄደው ትኬቱን እንደሚገዙ ነበር የተሰማሙት፡፡
የሚያደርገው ስላልነበረው ዕረፍት ለማድረግ አስቦ ጋደም አለ፡፡እንቅልፉ መኻል ላይ ያረፈበት ሆቴል ክፍል በር ሲንኳኳ ሰማ፡፡ የሚጠብቀው እንግዳ አልነበረም፤ ከፋይሰል በስተቀር ያረፈበትን ቦታ የሚያውቅ የቅርብ ሰው የለውም፡፡ ከፋይሰል ጋር ደግሞ ከሰኞ በፊት ሌላ ቀጠሮ አልነበራቸውም፡፡ በሰመመን ሆኖ የሆቴሉ ሰራተኞች ለፅዳት ወይንም ሌላ አገልግሎት መግባት ፈልገው ሊሆን እንደሚችል ገመተ፡፡ ከእንቅልፉ ጨርሶ መንቃት ስላልፈለገ የበሩን ጥሪ ትቶ ወደእንቅልፉ ለመመለስ ሞከረ፡፡ ከቆይታ በኋላ ግን በሩ እንደገና ተንኳኳ፡፡ ይኼው መንኳኳት እንደቀደመው ሊተወው የሚችለው አልነበረም፡፡ በከፍተኛ ድምጽ እና ቶሎ ቶሎ ነበር በሩ የሚደበደበው፡፡ በንዴት ሱሪውን እንኳን ሳያጠልቅ ከአልጋው ወረደና ወደበሩ ሄዶ ከፈተው፡፡ በሩ ላይ ቆመው መከፈቱን ይጠባበቁ የነበሩት ብዛት ያላቸው መሣርያ የታጠቁ ዥንጉርጉር ሰማያዊ መለዮ የለበሱ ሰዎች እና አንድ ሲቪል የለበሰ ሰው ፈረሃንን ገፍትረው ወደክፍሉ ገቡ፡፡ የሚያየውን ማመን ከብዶት ነበር፡፡ የታጠቁት ሰዎች የክፍሉን ጥግ ጥግ ይዘው ቆሙ፡፡ ሲቪል የለበሰው ሰውዬ የፈረሃንን ክንድ ይዞ እንዲቀመጥ ጎተተው፡፡ ሰውየው ቤቱን ዞር ዞር ብሎ ካየ በኋላ ፊት ለፊቱ ተቀመጠ፡፡ ሰውየው በተሰባበረ እንግሊዘኛ ፖሊሶች መሆናቸውን እና ያረፈበትን ክፍል ሊፈትሹ እንደሚፈልጉ ገልፆ ሻንጣዎቹን የት እንዳደረጋቸው ጠየቀው፡፡ ፈረሃን በአገጩ ወደሻንጣዎቹ ጠቆመ፡፡ ሰውየው በተጠንቀቅ ወደቆሙት ወታደሮች ዞሮ በዓይኑ ምልክት ሰጣቸው፡፡ ሁለቱ መሣሪያቸውን ወደጀርባቸው አዙረው አዘሉና ሻንጣዎቹን መበርበር ጀመሩ፡፡ ላፕቶፕ ኮምፒውተሩን፣ ለዘመዶቹ ይዟቸው የመጣው አራት ዘመናዊ ተንቀሳቃሽ ስልክ ቀፎዎች እና ሻንጣው ውስጥ ያገኟቸውን ወረቀቶች በሙሉ ለብቻ ለብቻ ዘረገፏቸው፡፡ ሲቪል የለበሰው ሰውዬ ወረቀቶቹን አለፍ አለፍ እያለ ገረበባቸው እና ወደፈረሃን ዞሮ ‹‹ፓስፖርትህ የት ነው ያለው?›› ሲል ጠየቀው፡፡ ፓስፖርቱን ከሱሪ ኪሱ አውጥቶ ሊሰጠው ከተቀመጠበት ፈረሃን ብድግ ሲል ሰውየው ከፍ ባለ ድምጽ ተቆጥቶ እንዲቀመጥ አዘዘው፡፡ ‹‹ፓስፖርቴ ያለው ሱሪ ኪሴ ውስጥ ነው፡፡›› አለ በድንጋጤ ተውጦ ሱሪው ወዳለበት ቁምሳጥን እየጠቆመ፡፡ ሰውየው እራሱ ሳጥኑን ከፍቶ ሱሪውን ፈተሸ፡፡ ጥቂት የኢትዮጵያ ብሮች፣ ብዛት ያለው የአሜሪካን ዶላር እና የአሜሪካን ዜጋ መሆኑን የሚያረጋግጥ ፓስፖርቱን ካወጣና ሌላ ምንም እንዳልቀረ ካረጋገጠ በኋላ ሱሪውን ለፈረሃን ወረወረለት፡፡ ፈረሃን በተቀመጠበት ሆኖ ታግሎ ሱሪውን አጠለቀ፡፡
ከሻንጣዎቹ የወጡትን ንብረቶቹን ለብቻ አድርገው ሻንጣዎቹን ዘግተው ይዘዋቸው ወጡ፡፡ ሲቪል የለበሰው ሰውዬ እንዲነሳ አዝዞ ወደበሩ በአገጩ ጠቆመው፡፡ ዝም ብሎ ከዚህ በላይ መሄድ ያልፈለገው ፈረሃን ምን እየተካሄደ እንደሆነ ጠየቀ፡፡ ሲቪል ከለበሰው ሰውዬ ‹‹ፖሊሶች ነን›› ከሚል ምላሽ ውጪ ምንም ተጨማሪ መረጃ ማግኘት አልቻለም፡፡ ገፍትረውት ከገቡት ክፍል እየገፉ ይዘውት ወጡ፡፡
***
የረፈሃንን ስልክ ጥሪ ተቀብሎ ለሰኞ ቀጠሮ ከሰጠው በኋላ ፋይሰል ወትሮ እሁድ ከሰዓት እንደሚያደርገው ከጓዶቹ ጋር ኳስ እየተጫወተ ለማሳለፍ ከሚኖርበት ቦሌ ሚካኤል የጋራ መኖርያ ቤቶች አቅራቢያ ወደሚገኘው የእግርኳስ ሜዳ አመራ፡፡ ቀድመውት ከደረሱት ጓደኞቹ ጋር ኳስ እየተጫወቱ ወደማጠናቀቁ ሲቃረቡ ያልተለመደ ሁኔታ አካባቢው ላይ አስተዋለ፡፡ ሁሉም ጓደኞቹ ቆመው ኳሷ ብቻዋን ሜዳው ላይ ተንከባለለች፡፡ አስር የሚደርሱ ፌደራል ፖሊሶች ኳስ መጫወቻ ሜዳውን ከበው እያጠበቡ እየተጠጓቸው ነበር፡፡ የፖሊሶቹ ጣቶች ያነገቡት መሣርያ ቃታ አካባቢ ተሰድሯል፡፡ ፋይሰል አብረውት ኳስ ከሚጫወቱት ጓደኞቹ መካከል አንደኛውን እንደሚፈልጉ ገምቶ ነበር፡፡ የመጡት ፖሊሶች ‹ፌደራሎች› መሆናቸው የመጡበት ጉዳይ ቀላል እናዳልሆነ ጠቁሞታል፡፡ ይህ እያሰላሰለ ለጥቂት ሰከንዶች ከገባበት ሐሳብ ስሙ ሲጠራ ሰምቶ ባነነ፡፡ የከበቧቸውን ፖሊሶች ከኋላ ሆኖ የሚመራው ሲቪል የለበሰ ሰውዬ ነበር ሥሙን የጠራው፡፡ በፍጥነት ነገሩ ሁሉ ተደበላለቀበት፡፡ ስሙ ድጋሚ ሲጠራ መደናገሩ ስላለቀቀው ቆሞ ከማፍጠጥ ውጭ ምንም ማድረግ አልቻለም፡፡ የጓደኞቹ ዓይኖች በሙሉ እሱ ላይ አነጣጠሩ፡፡ ለሦስተኛ ግዜ ስሙ ሲጠራ የሚማርበት ክፍል ውስጥ ጥያቄ ለመመለስ እንደሚያደርገው የግራ እጁን ወደላይ አነሳ፡፡
***
ሊነጋጋ ሲል ያደሩበት ክፍል በር ተከፍቶ በሽንት የተሞሉትን ላስቲኮች እያንጠለጠሉ እየተጣደፉ ሲወጡ ምን እንደተፈጠረ እንዲያስረዳው ፈረሃን ኡመድን ጠየቀ፡፡ በቀን ውስጥ ሽንቱን መሽናት እና ውሃ ለመቅዳት ከሚያገኛቸው ሁለት አጋጣሚዎች አነደኛው መሆኑን፤ ይህ አጋጣሚ ግፋ ቢል ለ20 ደቂቃዎች ብቻ ስለሚቆይ ፈጠን ብሎ ተነስቶ ጉዳዩን እንዲጨርስ ከማሳሰቢያ ጋር ኡመድ መለሰለት፡፡ ፈረሃን ያገኘው መልስ ባይዋጥለትም ማሳሰቢያውን ተቀብሎ ወደመጸዳጃ ቤቱ አመራ የሽንት ሰዓቱ አብቅቶ በሩ ተመል እንደተዘጋ ጉዳዩን እንዲያብራራለት በድጋሚ ኡመድን ጠየቀው፡፡ ኡመድ የተለየ መል አልነበረውም፡፡
ኡመድ እና ጓደኞቹ የፈረሃንን ቁርስ ተቀበሉለት እና አብሯቸው በላ፡፡ ሁሉንም በሥም ተዋወቃቸው፡፡ በዕድሜ፣ በተክለ ሰውነት፣ በፊታቸው ቀለም ይለያያሉ፡፡ ሁሉም እዛው የተዋወቁ እንደሆነ ገብቶታል፡፡ ነገር ግን ከእንቅልፉ ሲባንን ነጭ አንሶላ የመሰለ ልብስ ተከናንበው ቆመው በቃላቸው ሲያነበንቡ የነበሩት ሽማግሌ ሰውዬ ከትግራይ የመጡት ቄስ ጎይቶም፣ ከኡመድ ቀጥሎ ግርግዳውን ታክኮ ያለው ፍራሽ ላይ ለሁለት የተኙት ወጣቶች የጅማና የሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ ምህንድና ተማሪዎቹ ሌንጂሳ እና ቢልሱማ፣ ከራሱ በስተቀኝ በኩል ተኝቶ ያደረው ወጣት የ16 ዓመቱ የቤኒሻንጉል ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ ታጋይ አብዱ፣ ከሱ በተቃራኒው ከቄሱ አጠገብ የተኛው ጎስቋላ ጎልማሳ የቤጊው ገበሬው በሊስ (አስፋው)፣ ከነሌንጂሳ በተቃራኒ ያለውን ፍራሽ የሚጋሩት የጅማው ኢማም ሼህ ጀማል እና ጣሂር፣… ባጠቃላይ ከኤልያስ በስተቀር ሲገባ ከቆጠራቸው 13 ሰዎች ውስጥ 12ቱ በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በምርመራ ላይ ያሉ መሆናቸው ገና አልገባውም፡፡
ቁርሳቸውን ጨርሰው ሁላቸውም ፍራሾቻቸው ላይ ቁጭ ቁጭ ብለው በዝምታ ተዋጡ፡፡ ማታ ሲቀላቀላቸው በጨዋታ ደምቆ የነበረው ክፍል ለምን በዝምታ እንደተዋጠ አልገባውም፡፡ ምናልባት ወደኋላ እየሞቃቸው ሲሄድ ዝምታው እንደሚጠፋ ገመተ፡፡ በአብዛኞቹ ጭንቅላት ውስጥ ገብቶ ዝምታውን ያሰፈነው ሰኞ ጠዋት መሆኑ ነበር፡፡ እሁድ ቀን ከምርመራ ሚያርፉባት ናት፡፡ ሰኞ ጠዋት ደግሞ ምርመራው የቆመው ምን ጋር እንደነበር እያስታወሱ እንዴት እንደሚቀጥል እና ከግርፋት እና ከእንግልት የሚድኑበት መልስ ምን እንደሆነ የሚያሰላስሉባት ናት፡፡
ፈረሃን ዝምታን ለመስበር ለኡመድ ጥያቄ አነሳ፡፡ ‹‹አሁን ምንድነው የሚሆነው? ምንድን ነው የምሆነው?›› ኡመድ ረጋ ብሎ ለፈረሃን መመለስ ጀመረ ‹‹ዛሬ ምናልባት ፍርድ ቤት ይወስዱህ ይሆናል፡፡ ለምን እዚህ እንዳመጡህ ለፍርድ ቤት ሲያስረዱ ትሰማለህ …›› ፈረሃን ኡመድን አቋረጠውና ‹‹ፍርድ ቤት በእንግሊዘኛ ነው የሚሰራው?›› ሲል ጠየቀው፡፡ ኡመድ ፈገግ ብሎ ‹‹ፍርድ ቤት በእንግሊዘኛ አይሠራም፡፡ ሱማልኛ አስተርጓሚ መጠየቅ ግን ትችላለህ፡፡›› አለው፡፡ ማስረዳቱን ቀጥሎም ‹‹በደረቅ ወንጀል ከሆነ የጠረጠሩህ እስከ 14 ቀን የሚደርስ ቀጠሮ አለበለዚያ በሽብር የሚጠረጥሩህ ከሆነ ደግሞ …›› ፈረሃን በድጋሚ ኡመድን ቋረጠውና ‹‹ይህ ሊሆን አይችልም!›› አለ፡፡ ኡመድ ፈገግ ብሎ ‹‹በጣም ጥሩ›› ብሎ መለሰ፡፡ በልቡ ግን ፈረሃን ፍርድ ቤት ከሄደ የ28 ቀን ቀጠሮ ይዞ እንደሚመጣ ጠንካራ ግምት ነበረው፡፡
ትንሽ እንደተጨዋወቱ ያሉበት ክፍል በር ተከፈተና ኡመድ ተጠራ፡፡ እየተቻኮለ እየወጣ ወደፈረሃን ዞሮ ‹‹ምርመራ መሄዴ ነው፡፡›› አለው፡፡ ብዙም ሳይቆይ ፈረሃንም ተጠርቶ ወጣ፡፡ ለምሣ ሰዓት ጥቂት ግዜ ሲቀረው ፈረሃን ተመልሶ መጣ፡፡ ፊቱ ላይ የመቆጣት ስሜት ይነበብበት ነበር፡፡ ምርመራውን ጨርሶ ከፈረሃን በፊት ወደክፍሉ ተመልሶ የነበረው ኡመድ ‹‹ፈረሃን፤ እንኳን በደህና ተመለስክ፡፡ ፍርድ ቤት ወሰዱህ እንዴ?›› ሲል ጠየቀው፡፡ ተስፋ በቆረጠ የተሰላቸ ድምጽ ‹‹28 ቀን ቀጠሩኝ፡፡›› ብሎ ፍራሹ ላይ በደረቱ ተደፋ፡፡
***
የክፍሉ መቀርቀሪያ በኃይል ተወርውሮ ሲከፈት ያወጣው ድምጽ ሁሉንም ከእንቅልፍ ቀሰቀሳቸው፡፡ በርግጥ ከመካከላቸው ገና ወደበሩ እየቀረበ የነበረውን የእግር ኮቴ እና ሲንቀጫቀጭ የነበረውን የካቴና ድምጽ ሰምተው ከእንቅልፋቸው አስቀድመው የነቁ ነበሩ፡፡ በሩ ተከፍቶ ‹‹ሌንጂሳ አለማየሁ›› የሚል ድምጽ ተጣራ፡፡ ሁሉም ዓይናቸውን ወደሌንጅሳ ወረወሩ፡፡ ‹‹አቤት›› ብሎ ብርድ ልብሱን ከላዩ ላይ እየገፈፈ ተነሳ፡፡ ከመውጣቱ በፊት የመተኛ ሱሪው ላይ ሌላ ሱሪ ደረበ፡፡
ፈረሃን ክፍሉ ውስጥ የቀሩት ሰዎች ሌንጂሳን ያዩ የነበረበት ሁኔታ የሆነ ክፉ ነገር እንዳለ ነግሮታል፡፡ ከእንቅልፍ አስቀስቅሶ የሚያስወስድ አሳሳቢ ነገር ምን ይሆን ሲል አሰበ፡፡ ስንት ሰዓት እንደሆነ ጠየቀ፡፡ ኡመድ በግምት ሶስት ሰዓት አካባቢ እንደሚሆን ሲናገር ፈረሃን ቀና ብሎ የክፍሉን አራት ማዕዘን ግርግዳዎች ቃኘ፡፡ የፈለገውን አላገኘም፡፡ ‹‹እዚህ ምንም ሰው ሰዓት የለውም?›› ሲል ጠየቀ፡፡ ኤልያስ የፈረሃን ጥያቄ ያለአስተርጓሚ ስለገባው ተሰባበረ እንግሊዘኛ ወደማረፊያ ቤት ሰዓት ይዞ መግባት የተከለከለ መሆኑን አስረዳ፡፡ ፈረሃን የበለጠ ግራ በመጋባት ‹‹ታድያ የፀሎት ሰዓት ሲደርስ በምንድን ነው የምናውቀው?›› ኤልያስ ጥያቄውን መረዳት ስላቃተው የኡመድን ዓይን ያይ ጀመር፡፡ የኤልያስ ችግር የተረዳው ኡመድ የፈረሃንን ጥያቄ ተርጉሞ ነገረው፡፡ ‹‹አሃ…›› ኤልያስ መልሱን በእንግሊዘኛ ሲያደረጅ ቆየና ተሰላችቶ ኡመድን በቃ አንተ ንገረው በሚል አኳኻን አይቶት ዝም አለ፡፡ ጠዋት እና ማታ የሚቆጥሯቸው ፖሊሶች ሲመጡ ስንት ሰዓት እንደሆነ እንደሚጠይቋቸው እና ከዛ የቀረውን ግዜ በግምት እንደሚያሟሉት ኡመድ አብራራ፡፡ ፈረሃን ያለበት ቦታ ሲዖልነት ቀስ በቀስ እየገባው ነው፡፡ ቀጥሎ በጠየቃቸው ጥያቄዎች የተረዳው ነገር ደግሞ ለደህንነቱ አብዝቶ እንዲጨነቅ አስገደደው፡፡ ሌንጂሳ እና ጓደኛው ቢልሱማ ከሚማሩበት ዩኒቨርሲቲ በቁጥጥር ስር የዋሉት መንግሥት ሊተገብረው ያቀደውን የአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ ያሉ የኦሮሚያ ክልል ልዩ ዞኖች የተቀናጀ ማስተር ፕላንን በመቃወም የተካሄዱ ሰልፎች ላይ ተሳትፋቹኻል እና ተቃውሞውን አስተባብራቹኻል በሚል ምክንያት ሲሆን በተለይ ሌንጂሳ ጅማ ዩኒቨርስቲ ደጃፍ ላይ በደህንነቶች ከተያዘ በኋላ አዲስ አበባ እስኪመጣ ድረስ የነበረውን 3ቀን እህል የሚባል እንዳልቀመሰ፣ አሁን ያሉበት ቦታ ካመጡት ጀምሮ ደግሞ በየቀኑ ማታ ማታ ተጠርቶ ሌሊቱን ክፉኛ እየተደበደበ በምርመራ እንደሚያጋምስ ነበር የተነገረው፡፡ ምርመራ ተወስዶ መደብደብ ማንም ሰው ላይ ሊከሰት እንደሚችል፣ ክፍሉ ውስጥ ከነበሩት ሰዎች መካከል ጨዋታ ከሚወደው ባለ ደንዳና ሰውነቱ የቡና ነጋዴ ኤልያስ በስተቀር ሁሉም ክፉኛ ድብደባ የደረሰባቸው መሆኑን ኡመድ አንድ በአንድ እየጠቆመ ነገረው፡፡
እንቅልፍ አጥቶ ሲገላበጥ ብዙ ሰዓት አለፈው፡፡
የክፍሉ በር ተከፈተና ሌንጂሳ በፖሊስ ተደግፎ ወደክፍሉ ገባ፡፡ እራሱን ችሎ መራመድ ስላቃተው ቢልሱማ ተነስቶ ድጋፍ ሆኖት ወደፍራሹ አደረሰው፡፡ ሁሉም ድጋሚ ከእንቅልፋቸው ተነስተው በትካዜ ተዋጡ፤ የተከሰተው ለሁሉም ገብቷቸዋል፡፡ ፈረሃን አንድ ነገር ድንገት ጭንቅለቱ ውስጥ አቃጨለ፡፡ አንድ ጓደኛው ከወራት በፊት በአግራሞት አውርቶለት የነበረ ‹‹Human Rights Watch›› የተባለ የመብት ተሟጋች ቡድን ‹‹They Want Confession›› በሚል ርእስ ያወጣው ዘገባ ትዝ አለውና ወደኡመድ ዞሮ ‹‹ማዕከላዊ ነው እንዴ ያለነው?›› ሲል ጠየቀ፡፡
***
ፋይሰል ፍርድ ቤት የተከሰተው ነገር ጭራሽ ግርታውን አብሶበታል፡፡ ከሱ እና ከአጎቱ ልጅ በተጨማሪ አይቷቸው የማያውቃቸው ሶስት ወንድ እና አንድ ወጣት ሴት ሱማሌዎች አብረዋቸው ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡ ሶስቱ ወንድ ሱማሌዎች የሚያመሳስላቸው ነገር እንዳለ ፋይሰል አስተውሏል፡፡ የአነጋገር ዘይቤያቸው ልክ እንዳጎቱ ልጅ ውጭ ሀገር ቆይተው እንደመጡ ያስታውቃል፡፡ 18 ዓመት እንኳን የሞላት የማትመስለው አብራቸው ፍርድ ቤት የቀረበችው ሴት ደግሞ ከአነጋገሯ የኢትዮጵያ ሱማሌ እንዳልሆነች ገብቶታል፡፡
ከፍርድ ቤት እንደተመለሰ ክፍሉ ውስጥ የነበሩት ሰዎች ጥያቄ ያጣድፉት ያዙ፡፡ ፍርድ ቤት የተከሰተውን ለማስረዳት ሞከረ፡፡ ስድስት ሆነው እንደሄዱ፣ ችሎት ውስጥ ለሁለት ከፍለው ሦስት ሦስት አድርገው ይዘዋቸው እንደገቡ፣ እሱን በዕድሜ ሸምገል ካለው ሰውዬ እና ከወጣቷ ጋር ችሎት ፊት እንዳቀረቡት ነገራቸው፡፡ በጥሞና ሲያዳምጡት የነበሩት ሰዎች በምን ወንጀል እደተጠረጠረ ለማወቅ ነበር፡፡ ፋይሰል በረጅሙ ትንፋሽ ወስዶ ‹‹አል ሸባብ ከተባለ ቡድን ተልዕኮ ተቀብለው አዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የሽብር ወንጀል ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ ይዣቸኋለው፡፡›› የሚል ክስ ይዟቸው የሄደው ፖሊስ አንብቦ የ28 ቀን ቀጠሮ እደጠየቀና መነፅራቸውን ዝቅ አድርገው ጥያቄውን የሰሙት አዛውንት ሴት ዳኛ የ28 ቀን ቀጠሮውን መፍቀዳቸውን አስረዳቸው፡፡ ከጠበቁት ብዙም የራቀ ነገር አልነገራቸውም፡፡ ምንም የመደንገጥም ሆነ የመሸሽ ዓይነት ስሜት ስላላየባቸው እረፍት ቢሰማውም ሽብርን የሚያክል ትልቅ ክስ ቀረበብኝ ሲላቸው አለመገረማቸው ግር አሰኝቶት ነበር፡፡ ኋላ ላይ ሲረዳ ግን ማዕከላዊ የገባ ሰው ከሱማሌ ከሆነ አልሸባብ ወይንም ኦብነግ ተብሎ፣ ኦሮሞ ከሆነ ኦነግ፣ ከትግራይ ከሆነ ትሕዴን፣ ሙስሊም ከሆነ አልቃይዳ፣ አማራ ከሆነ አርበኞች ግንባር፣ ጋዜጠኛ ወይንም የፖለቲካ ድርጅት አባል ከሆነ ግንቦት 7 ተብሎ መከሰሱ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡
***
ምሣ በልተው እንደጨረሱ በሩ ተከፈተና የፋይሰል ስም ተጠራ፡፡ ‹‹አለሁ›› ሲል ለጥሪው መልስ፡፡ ‹‹ዕቃህን ይዘህ ውጣ›› የሚል ትዕዛዝ ተከተለ፡፡ የተባለው ስላልገባው እንዲደገምለት ‹‹እእ…›› አለ፡፡ በሩ ላይ የቆመው ፖሊስ ቁጣ በተቀላቀለበት ድምጽ ‹‹ዕቃህ ይዘህ ውጣ!›› ሲል ደገመለት፡፡ ከኳስ ጨዋታው መልስ ታጥቦ ሊቀይር ይዞት የነበረውን ልብስ በስስ ፌስታል ይዞ ወጣ፡፡
በር ላይ ቆሞ የነበረው ፖሊስ ካቴና አለመያዙን ሲያስተውል ተስፋ ቢጤ ተሰምቶት ነበር፡፡ ግን የተሰማው የተስፋ ስሜት በፍጥነት ወደተስፋ መቁረጥ ተለወጠ፡፡ ከሰው ጋር አብሮ ይታርሰር ከነበረበት ማረፊያ ቁጥር 9 የወጣው ብቻውን ወደሚታሰርበት ጨለማ ክፍል ቁጥር 8 ለመዘዋወር ነበር፡፡
***
በተለምዶ ሳይቤሪያ ተብሎ የሚጠራው የማዕከላዊ ሕንጻ ቁጥር 84 በረጅም ኮሪደር ለሁለት የተከፈለ ሲሆን የእስረኛ ማቆያ ክፍሎቹ ከኮሪደሩ ግራና ቀኝ የተደረደሩ ናቸው፡፡ ኮሪደሩ ሲጀመር በግራና በቀኝ 2ቁጥር እና 10 ቁጥር ማረፊያ ክፍሎች ፊት ለፊት ተፋጠዋል፡፡ በግራ በኩል ከ2ቁጥር አንስቶ እስከ 6ቁጥር የሚዘልቅ ሲሆን በስተቀኝ በኩል ደግሞ ከ10 ቁጥር ጀምሮ ቁልቁል እየቆጠረ እስከ 7ቁጥር ይሄዳል፡፡ ከ7 ቁጥር ማረፊያ ክፍል ቀጥሎ ደግሞ ዘጠኙ ክፍሎች ውስጥ የሚታሰሩት ሰዎች በየተራ ክፍሎቹ እየተከፈቱ በቀን ሁለት ግዜ (ጠዋት እና ማታ) ቢበዛ ለ20 ደቂቃዎች የሚጠቀሙበት ባለ6 የሽንት ቤት ክፍል እና አንድ መታጠቢያ ክፍል ያለው መጸዳጃ ቤት ይገኛል፡፡
ሳይቤርያ ውስጥ የሚገኙት ክፍሎች በስፋት ካልሆነ በቀር አንድ ዓይነት ናቸው፡፡ ከሁሉም ክፍሎች የሚለየው 8ቁጥር ነው፡፡ ከውጪ በሩ ተዘግቶ ለሚያየው ሰው 8 ቁጥርም ቢሆን ከሌሎቹ የሚለይበት ነገር የለም፡፡ በሩ ተከፍቶ ወደውስጥ ሲገባ ግን በግራና በቀኝ በኩል ሁለት ሁለት የራሳቸው በር ያላቸው ሌላ ከፍሎች ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ክፍሎች ጠንከር ያለ ምርመራ እየተደረገባቸው ላሉ መንፈሰ ጠንካራ ሰዋች የተዘጋጀ ነው፡፡ እነዚህ ክፍሎች ውሰጥ የሚታሰር ሰው በቦታ ጥበት፣ በጨለማ እና ብቸኝነት ይፈተናል፡፡

ይህ ታሪክ ለአንባቢ ምቾት ሲባል ከተደረገለት ዘይቤያዊ ማስተካከያ በስተቀር እውነተኛ ታሪክ ነው፡፡

(ይቀጥላል)

The post ‹‹ማዕከላዊ ነው እንዴ ያለነው?›› (ክፍል ፩) በናትናኤል ፈለቀ appeared first on Zehabesha Amharic.

ፍ/ቤቱ በአቶ ዮናታን ተስፋየ ላይ ለ2ኛ ጊዜ 28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ሰጠ

0
0

‹‹ነጻነት ይሰማኛል›› ዮናታን ተስፋየ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብር ወንጀል ተጠርጥሮ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ማዕከል በእስር ላይ የሚገኘው የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለ2ኛ ጊዜ የ28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶበታል፡፡

yonatan Tesfaye
ዛሬ ጥር 17/2008 ዓ.ም አራዳ ፍርድ ቤት የቀረበው አቶ ዮናታን ፖሊስ ምርመራየን አልጨረስኩም በሚል የጠየቀበትን ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ በመፍቀድ ለየካቲት 15/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ አቶ ዮናታን ተስፋየ የዋስትና መብቱ እንዲከበርለት ቢጠይቅም ፍርድ ቤቱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡
ፖሊስ በአቶ ዮናታን ላይ ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ሲጠይቅ ‹‹የቴክኒክ መረጃዎችን መሰብሰብ ይቀረናል፤ ያልተያዙ ግብረ አበሮችንም አሉ›› የሚል ምክንያት ማቅረቡን የተጠርጣሪ ጠበቃ ገልጸዋል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋየ በጠበቃ እና በቤተሰቦቹ እንዳይጎበኝ እንደተከለከለና ከታሰረበት ክፍል መታፈን የተነሳ የጤና እከል ቢገጥመውም ህክምና እንዳላገኘ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ ፍርድ ቤቱም አቤቱታውን አድምጦ በጠበቃውም ሆነ በቤተሰቦቹ እንዲጎበኝ እንዲፈቀድለትና ህክምናም እንዲያገኝ ትዕዛዝ መስጠቱን ከጠበቃው ለማወቅ ተችሏል፡፡
አቶ ዮናታን ከችሎት ሲወጣ በስፍራው ለነበሩት ቤተሰቦቹና ወዳጆቹ ያለውን ፍቅር ገልጾ ‹‹ነጻነት ይሰማኛል›› በማለት ጮክ ብሎ ሲናገር ተደምጧል፡፡

The post ፍ/ቤቱ በአቶ ዮናታን ተስፋየ ላይ ለ2ኛ ጊዜ 28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ሰጠ appeared first on Zehabesha Amharic.

በሚኒሶታ የሰብአዊ መብት ታጋይና የቀድሞው የNAACP ፕሬዚዳንት ታዬ ረታ አረፉ

0
0

Taye Reta
(ዘ-ሐበሻ) ታዋቂው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ አቶ ታዬ ረታ እዚሁ ሚኒሶታ ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ማረፋቸውን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመልክቷል::

በሚኒሶታ ሴንት ክላውድ ከተማ የNational Association for the Advancement of Colored People (NAACP) ፕሬዚዳንት በመሆን በተለይ በአሜሪካን ሃገር ለሚኖሩ ጥቁሮች ከፍተኛ የሆነ ትግል ሲያደርጉ የቆዩ ነበሩ:: በሚኒሶታ የኢትዮጵያ ኮምዩኒቲና በቤተክርስቲያናት ምስረታዎች ላይ ከፍተኛውን አስተዋጽኦ እንዳደረጉ የሚነገርላቸው አቶ ታዬ ማረፋቸው ከተሰማ በኋላ ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጆቻቸው የፍትሃታቸውን እና የቀብራቸውን ሁኔታ በማመቻቸት ላይ ናቸው::

ዘ-ሐበሻ ተጨማሪ መረጃዎችን ይዛ ትመለሳለች::

 

አቶ ታዬ ለመጨረሻ ጊዜ በፍኖተ ጥበብ ዓመታዊ በዓል ላይ ያቀረቡት ግጥምን ልትውስታ አድምጡት::

The post በሚኒሶታ የሰብአዊ መብት ታጋይና የቀድሞው የNAACP ፕሬዚዳንት ታዬ ረታ አረፉ appeared first on Zehabesha Amharic.

ጃዋር መሐመድ ተናገረ “ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግለጫ ማውጣታቸውን አቁመው ሕዝቡን የማስነሳት ሥራ መስራት አለባቸው”አለ |የሚደመጥ ቃለምልልስ

0
0

“የአውሮፓ ሕብረት መግለጫ ለኦሮሞ ሕዝብ ጭቆና ምስክርነት የሰጠበት ነው”

“ተቃዋሚዎች ስም ብቻ ደርድረው መቀመጥ ብቻ አይደለም:: ጠጠር መወርወር አለባቸው”

“መሪ ከላይ ቁጭ ብሎ ታች ያለውን ሕዝብ እንዲህ አድርግ እያለ የሚያዝበት የትግል ጊዜ አልፏል”
“ወያኔ ካሁን በኋላ የኦሮሞን ሕዝብ አስከትዬ እሄዳለሁ የሚል ከሆነ ተሳስቷል”
“የጎንደር ለም መሬት ለሱዳን መሰጠቱን ተከትሎ ሕዝቡ ያነሳውን ተቃውሞ ወደ ጎጃምም እንዲስፋፋ…”
“ይህን ትግል የሚያንቀሳቅሱት ልጆች ከወያኔ በእውቀትም በብልጠትም የተሻሉ ናቸው”
“ለማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲዎች ልምዳችንን ለማካፈል ዝግጁ ነን”

(ዘ-ሐበሻ) የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ዳይሬክተር ጃዋር መሐመድ ከሕብር ራድዮ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ ጋር ባደረገው ልዩ ቃለምልልስ ተቃዋሚዎች የመግለጫ ጋጋታቸውን አቁመው ህዝቡ ውስጥ ገብተው እንዲሰሩና በኦሮሚያ ክልል ከተነሳው ሕዝባዊ ቁጣ እንዲማሩ ጠየቀ:: “አሁን ትግሉ ከላይ ቁጭ ብለህ ታች ያለውን ሕዝብ እንዲህ አድርግ እያልክ የምታዝበት ጊዜ አይደለም… ታች ወርዶ መታገልን ይጠይቃል” ያለው ጃዋር በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ ቁጣ ማቆሚያ የለውም ገና ይቀጥላል ብሏል:: የጎንደር ለም መሬት ለሱዳን መሰጠቱን ተከትሎ ሕዝቡ ያነሳውን ተቃውሞ እንደምሳሌነት ያነሳው ጀዋር የፖለቲካ ፓርቲዎች መግለጫ ማውጣታቸውን ትተው የጎንደርንም; የጎጃምንም ሌላውንም ሕዝብ ወደ ማስነሳቱ ሥራ መግባት ይኖርባቸዋል ብሏል:: ሙሉ ቃለምልልሱን አዳምጡት::

Jawar Mohamed

The post ጃዋር መሐመድ ተናገረ “ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግለጫ ማውጣታቸውን አቁመው ሕዝቡን የማስነሳት ሥራ መስራት አለባቸው” አለ | የሚደመጥ ቃለምልልስ appeared first on Zehabesha Amharic.

‹‹የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል›› እስክንድር ነጋ –በላይ ማናዬ

0
0

Eskinder Nega(ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በነገው ዕለት ለዘላለም ወርቃገኘሁ መከላከያ ምስክር ሆኖ ልደታ ፍርድ ቤት ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ይህን በማስመልከት ህዳር 19/2007 ዓ.ም ለ10 ደቂቃዎች ያህል እስክንድርን ቃሊቲ ስናገኘው የተናገረውን በሚመለከት ከተጻፈው ለማስታወስ….)

በላይ ማናዬ

‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል!››

ይህን ያለው ትንታጉ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ነው፡፡ እስክንድር ነጋን ካወኩት ወዲህ እንደዛሬ በኃይለ ቃል ሲናገር ሰምቼው አላውቅም፤ ወይም ትዝ አይለኝም፡፡ ህዳር 19/2007 ዓ.ም እኩለ ቀን ላይ እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ተገኝቼ ነበር፡፡ ሆኖም ሁኔታው ሁሉ እንደማንኛውም ቀን አልነበረም፡፡ በር ላይ ስደርስ በርከት ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት ሰሞኑን እያካሄዱት ያለውን የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በማስመልከት እስክንድር ነጋን፣ አንዱዓለም አራጌን እና ሌሎችንም ሊጠይቁ በቦታው ተገኝተው ነበር፡፡

በጠዋት ቂሊንጦ የሚገኙ ወዳጆቼን ጠይቄ አብረውኝ ከነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ጋር ነበር ወደ ቃሊቲ ያመራሁት፡፡ ቃሊቲ የተገኘው ሰው ሁሉ መጠየቅ የሚፈልገውን ሰው እና ሙሉ አድራሻውን እያስመዘገበ ሳለ በመሐል እኔም እስክንድርን መጠየቅ እንደምፈልግ ነግሬ ተመዘገብኩ፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ግን ስማችሁ ከዚህ ቀደም ያልተመዘገባችሁ አሁን መግባት አትችሉም መባሉን መዝጋቢ ፖሊሱ አረዳን፡፡ እኔ እና ትንሽ ሰዎች መግባት ስንችል አብዛኛው ሰው ግን መግባት እንደማይችል ተነገረን፡፡

በዚህ ሁኔታ እስክንድር ጋር ደርሰን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ አንድ የአንድነት ፓርቲ አባል ሰሞኑን ፓርቲያቸው እስረኞችን በተመለከተ በማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ እየተሰራ ያለውን ስራ ለእስክንድር ያብራራለት ጀመር፡፡ እስክንድር በተለመደ ጥሞናው ሲያዳምጠው ቆይቶ፣ በግሉ የተሰማውን እና መሆን ቢችል ያለውን ነጥብ ተናገረ፡፡ በመሐል ወጣቱ የአንድነት አባል ወደ እስክንድር ጠጋ ብሎ ሌሎች ተጨማሪ ጉዳዮችን ሲነግረው ድንገት አንድ የፖሊስ አዛዥ ጨዋታቸውን እንዲያቆሙና እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እንዲገባ፣ ወጣቱ የአንድነት አባል ደግሞ ወደ ውጪ እንዲወጣ በትዕዛዝ ማጣደፍ ያዘ፡፡

ይህኔ እስክንድር ለስለስ ባለ አነጋገር ምንም እንዳላጠፋን በመግለጽ ፖሊሱ መረጋጋት እንዳለበት አስረዳ፡፡ የፖሊስ አዛዡ ግን ጭራሽ ብሶበት ወጣቱ በቶሎ እንዲወጣ አደረገ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ‹ፖለቲካ ማውራት አቁሙ› የሚል ሆነ፡፡ ይህን ተከትሎ እስክንድር ድንገት በኃይለ ቃል ተናገረ፡፡ ‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው!›› አለ እስክንድር በስሜት ውስጥ ሆኖ፡፡

በግሌ እስክንድር እንዲረጋጋ፣ ሁኔታው ግን ያልተገባ እንደሆነ ገለጽኩ፡፡ ፖሊሱ ግን ሊረጋጋ አልቻለም፡፡ እስክንድርን ይዞት ሄደ፡፡ ‹‹በርቱ! እንቅስቃሴያችሁ ህጋዊና ሰላማዊ ይሁን እንጂ ትግላችሁን ቀጥሉ!›› ሲል እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እየገባ ተናገረ፡፡ የፖሊስ አዛዡም ከእስክንድር ጋር የነበረንን ቆይታ ሰዓቱ ሳይደርስ ገታው፡፡ የእስክንድር ያገባኛል ባይነት አስደመመኝ፡፡ እስር ቤት ሆኖም፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም እስክንድር ስለ ሀገሩ እንደሚያገባው በስሜት ተናገረ፡፡ መብቱን መቼም ቢሆን አሳልፎ እንደማይሰጥ አስረገጠ፡፡

ስለ ያገባኛል ባይነት ሳስብ በጠዋት ቂሊንጦ ያገኘኋቸውን የዞን 9 ጦማሪዎች አስታወስኩ፡፡ ‹ስለሚያገባን እንጦምራለን!› ይላሉ ወጣቶቹ ጦማሪያን፡፡ ከአብርሃ ደስታ ጋር አብረው ያገኘኋቸው እነ በፍቃዱ ኃይሉ እና አጥናፍ ብርሃኔ ብዙ ጉዳዮችን እያነሱ አወጉኝ፡፡ ‹‹ህወሓት አንድ ወይም ሁለት ነባር የህወሓት ባለስልጣናትን በሽብር ከከሰሰ ስርዓቱ እንዳበቃለት እቆጥራለሁ፡፡ ምክንያቱም ሽብር ማታለያ መሆኑ ይቀራል›› አለኝ በፍቃዱ ኃይሉ፡፡ አብርሃ ደስታ ቀበል አድርጎ ‹‹እናት አልጋነሽ በሽብር ስትከሰስ በጣም ብዙ ሰው ተቃውሞ ነበር›› አለ፡፡ አጥናፍ በበኩሉ ‹‹ቄስና ሸህ ሽብርተኛ እየተባለ አይደለም እንዴ›› በማለት ጠየቀ፡፡

አብርሃ ደስታ አንድ ነገር በኃይል እንደሚቆጨው ተናገረ፡፡ ምን እንደሆነ ጠየቅሁት፡፡ ‹‹ብዙ የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ሳላደርግ መታሰሬ ይቆጨኛል!›› አለ፡፡ በፍቃዱ በበኩሉ፣ ‹‹እኔም የገባኝ ነገር ያለውን የሰላማዊና ህጋዊ የመስሪያ ልክ አለመስራታችን ነው፡፡ አሁን ላይ ሆኜ ሳስበው እንዲህ ለሚያስሩን ስንት ህጋዊና ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን እንኳ ሳናደርግ በትንሽ ነገር በርግገው እዚህ ሲያስገቡን ይቆጨኛል›› በማለት ሀሳቡን ቀጠለ፡፡ ‹‹በእርግጥ አንድ ሰው አሁን መጠንቀቅ ያለበት የሚሰራው ስራ ህጋዊ መሆን አለመሆኑን እንጂ፣ ይህን ካደረኩማ ያስሩኛል የሚለውን መሆን የለበትም፡፡ እነሱ ከፈለጉ ያስሩሃል፤ ስለዚህ መብትህን ተጠቅመህ መታሰሩ ይሻላል እንዲሁ ምንም ሳይሰሩ ከመግባት›› ሲል አብርሃ ሀሳቡን አካፈለ፡፡

ቂሊንጦ ከእነ በፍቃዱ ጋር ስንጨዋወት ስለእስክንድር ነጋ ትሁትነት፣ አስተዋይነት፣ ሰላማዊነት እያነሱ ሰላምታ እንዳደርስላቸው ጠየቁኝ፡፡ እኔም እስክንድር ነጋን ሳውቀው በትሁትነቱ፣ በአስተዋይነቱና በሰላማዊነቱ ነው፡፡ ዛሬ በነበረው ሁኔታ ግን ክፉኛ ተበሳጭቶ ነበር የተመለከትኩት፡፡ ያ ፈገግታው ከፊቱ ብን ብሎ ጠፍቶ ‹‹ያገባኛል!›› ሲልበት የነበረውን ስሜት ግር አለኝ፡፡ ካልነኩት የማይነካ ሰው ሲነኩት ትንታግ ነው፡፡ እስክንድር እዛ ስሜት ውስጥ የገባው ተገድዶ ነበር፡፡ ሊጠይቁት የመጡትን ሰዎች አብዛኞቹን አላስገባም ማለታቸው ሳያንስ ከገቡትም መካከል የምታወራውን እኔ ልምረጥልህ በሚል ግብዝነት አባርረዋል፡፡ እስክንድር ይህን አይቶ ዝም ማለት አልቻለም፡፡ ስለሆነም እንዲህ አለ፤ ‹‹…እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው! ስለሀገሬ ያገባኛል!››

The post ‹‹የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል›› እስክንድር ነጋ – በላይ ማናዬ appeared first on Zehabesha Amharic.

የአባይ ፀሃዬ የለውበትም የት ያደርስ ይሆን? –ግርማ ሰይፉ

0
0

የአባይ ፀሃዬ የለውበትም የት ያደርስ ይሆን?

girmaseifu32@yahoo.com; www.girmaseifu.blogspot.com

Abay Tsehaye - satenawወዳጆች መቼም የዚህ ሀገር ነገር ግራና ቀኙ ጠፍቶዋል እንበል እንዴ? የፌዴራል ሹሞች የበታች ሹሞችን በፖለቲካ ውሳኔ በሚመጡ ጉዳዮ ጭምር እጃቸውን ወደታች መቀስር ጀምረዋል፡፡ ይህ ጉዳይ አዲስ አይደለም፡፡ ከዚህ በፊትም አማርኛ ተናጋሪዎች ተለይተው ከመኖሪያቻው ሲፈናቀሉ፣ ተጠያቂ የተደረጉት “ጥቂት ኪራይ ስብሳቢ” የተባሉ የበታች ሹሞች ናቸው፡፡

አሁን ደግሞ የአዲስ አበባና በዙሪያ ያሉ ከተሞች የተቀኛጀ ማስተር ልማት ይዞት የመጣው ጦስ በቀላሉ የሚገላገሉት አይመስልም፡፡ ጎምቱ የሚባሉት ባለስልጣናትም ቢሆን ስህትት ከመስራት የሚያግዳቸው ኃይል ሊገኝ አልቻለም፡፡ የዛሬ ፅሁፌ መነሻ የሆነው ደግሞ አቶ አባይ ፀሃዬ በሚዲያ የሰጡት የመከላከያ መልስ እጅግ ስለአስገረመኝ ነው፡፡

ባጠቃላይ መንግሰት የሚባለው አካል እንደ አካል ይህ ጦሰኛ የተቀናጀ ማስተር ፕላን ግራ አጋብቶታል፡፡ ግራ ተጋብቶ ግራ እያጋባን ይገኛል:: የአዲስ አበባ መሰተዳደር በግሉ ማስተር ፕላኑን ተግባራዊ ያደርጋል የሚል ዜና የሰማነው የኦሮሚያ/የኦህዴድ ሰራ አስፈፃሚ የተቀናጀ ማስተር ፕላኑን ተግባራዊ እንዳይሆን ውድቅ ባደረገ ማግስት ነው፡፡ አዲስ አበባ በተናጥል ማስተር ፕላኑን ተግባራዊ ሲያደርግ በዙሪያ ያሉት ከተሞች ላይ የሚያሰከትለው በጎም ሆነ አሉታዊ ተፅህኖ እንዴት እንደሚታይ የነገረን የለም፡፡ ለማነኛውም ይህን እናቆይ እና ለፅሁፌ መነሻ ወደ ሆነው ጉዳይ ልግባ፡፡

በእኔ እምነት በኦሮሚያ አካባቢ ለተነሳው ንቅናቄ ዋነኛው ነገር ቆስቋሽና አቀጣጣይ የነበሩት አቶ አባይ ፀሃዬ ናቸው ብዬ አምናለሁ፡፡ አሁን ደግሞ ኦቶ አባይ ፀሃዬ እጅ እና እግር የለሌለው ክስ በየደረጃው ወደሚገኙት የኦሮሞ ካድሬዎች ላይ አቅርበዋል፡፡ ወደዚህ ጉዳይ በዝርዝር ከመግባቴ በፊት ግን በዚህ ጦሰኛ ማስተር ፕላን ነገር ቆስቋሽና አቀጣጣይ ያልኩበትን ምክንያት ማስረዳት ይኖርብኛል፡፡

አቶ አባይ ፀኃዬ በአሁኑ ሰዓት ያላቸው ስልጣን ጠቅላይ ሚኒስትሩን በፖሊሲና ጥናት ጉዳዮች ማማክር እንደሆነ ይታወቃል፡፡ እንደሚታወቀው ይህ ስልጣና በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር የስልጣን ዘመን የነበረ አይደለም፡፡ ኦቶ አባይ ይህንንም ስልጣናቸውን የገለፁበት መንገድ ጠብ የሚፈልግ ካለ ወይም ከተገኘ ለጠብ የሚመች ነው፡፡ “ጠቅላይ ሚኒስትር የእለት ተእለት ስራ ስለሚበዛባቸው በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ እንደንስራ ተመደብን” ሲሉ በመጀመሪያ ያድረኩት የህገ መንግሰቱን አንቀፅ 79 መመልከት ነበር፡፡ ይህ ህገ መንግስት ካልተቀየረ በሰተቀር የፖሊሲ ጉዳዮችን ሸክም የሚወስድላቸው ሌላ ሰው መድበው እርሳቸው በሌላ የእለት ተዕለት ስራ መጠመድ አይገባቸውም ነበር፡፡ አቶ አባይ ፀሃዬ በዚሁ ስልጣናቸው መነሻ ባለፈው ሁለት ዓመት ግድም በኦሮሚያ በተለይ አምቦ አካባቢ በተነሳው ግርግር ማግስት ቆም ብሎ የነበረውን የተቀናጀ ማስተር ፕላን ጉዳይ ከምርጫው በኋላ በአሸናፊነት መንፈስ ከኦህዴድ ካድሬዎች ጋር ባደረጉት ውይይት “ይህንን ፕላን በግዳቹ ትተግባራለችሁ ብለዋል የሚለው ነው”፤ ይህን አይሉም ሊባል የማይችለው የኦህዴድ ባለስልጣናትም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የነበራቸው አቋም ተግባራዊ ለማድረግ ምን እናድርግ? የሚለው እንጂ ተግባራዊ አናደርግም የሚል ሰለ አልነበረ ነው፡፡

ይህች በግድ የምትል ቃል እልህ አስገብታ ይህን ሁሉ እሳት የጫረች እንደሆነች መገንዘብ አያሰቸግርም፡፡ ከአቶ መለስ ዜናዊ እልፈት በፊት ኦሮሚያ በእጅ አዙር ይቆጣጠሩት እንደነበር፤ ለዚህም እንደ አለማየሁ አቶምሳ እና ሙክታር የመሰሉ የመለስ ቀኝ እጆች እንደነበሩ ይታወሳል፡፡ ሉሎችም አሉ፡፡ ከመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ የኦሮሚያ ባለስልጣናት ከህውሃት ሰዎች ጋር ትከሻ መለካከት እንደጀመሩ ብዙ ማሳየዎች አሉ፡፡ አቶ አባይ ፀሃዬ ከመለስ ሞት ማግስት ጀምሮ ከአንገታቸው ቀና ካሉት ሰዎች አንዱ ቢሆኑም በኦሮሚያ ሰፈር የተፈጠረውን ትከሻ መለካካት ያጤኑት አይመስለኝም፡፡ይህን ትከሻ መለካካጽ ልብ ብለውት ቢሆን ኖሮ “በግዳችሁ ትተገብራላችሁ” የምትለው ጦሰኛ ቃል አትውጣም ነበር፡፡ በግድ ማርም ቢሆን አይጥምም!!!

በእኔ እምነት አሁን በኦሮሚያ አካባቢ የተነሳው በዋነኝነት “እምቢ ማስተር ፕላን” ተቃውሞ በኦሮሚያ በሚገኙ ኦህዴድ ካድሬዎች ቀጥተኛ ድጋፍ እንዳለው ምንም ጥርጥር የለኝም፡፡ ድጋፋቸውን የሚሰጡበት መንገድ የተለያየ ቢሆንም፡፡ ኦህዴድ ዛሬ እንደ ከዚህ ቀደሙ በኢህአዴግ በሚቀመጥለት አቅጣጫ የኦህዴድ ካደሬዎችን አፍሶ እስር ቤት ማሰገባት የሚችል አይመሰለኝም፡፡ ዶክተረ ነጋሶ በአንድ ወቅት እንደነገሩን በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ካድሬዎችን አባረው እና እስር ቤት አስገብተዋል፡፡ የዚያን ጊዜው ኦህዴድ አሁን ያለ አይመስለኝም፡፡ የአሁኑ ኦህዴድ ያለው እድል ካድሬዎቹን ተለማምጦ በስልጣን መቆየት ነው የሚኖርበት፡፡ ሰለዚህ አቶ አባይ እንዳሉት በግድ መተግበር ሳይሆን ማስተረ ፕላኑን መሰረዝ ነው፡፡

አቶ አባይ ፀሃዬ እራሳቸውን ሲቀጥልም እናት ፓርቲያቸውን ሕውሃትን ለመከላከል ብለው የሰጡት ምለሽ በእርግጥ ሌላ ዙር ቀውስ የሚጠራ ነው፡፡ ይህ የአባይ ፀሃዬ የለውበትም መልስ የት እንደሚያደርስ ግን አላውቅም፡፡ መልሳቸው ባጠቃላይ አሁን በኦሮሚያ አካባቢ የተነሳው ንቅናቄ መንስዔ “በኦሮሚያ የተለያየ እርከን የሚገኙ የኦህዴድ ሹሞች ሌቦች በመሆናቸው፣ ህዝቡ የሚጠይቀውን የመልካም አስተዳድር ምላሽ መሰጠት ባለመቻላቸው፣ ወዘተ” የሚል ነው፡፡ በዚህ የመከላከያ መልሳቸው በቀጥታ ላለመንካት የፈለጉት የኦህዴድ ከፍተኛ ሹሞችን ብቻ ነው፡፡ በእኔ እምነት ከወረዳ እሰከ ዞን ብሎም ክልል ድረስ ያሉት ሹሞች ሃላፊነት የተሰጣቸው በኦህዴድ ከፍተኛ ሹሞች ነው፡፡ በክስ ውስጥ ሊዘሏቸው ቢፈልጉም የበታቾቻቸውን መከላከል ወይም አብረው መከሰሳቸው መረዳት ግድ ነው የሚሆነው፡፡ የኦህዴድ ባለስልጣናት አቶ አባይ ፀሓዬን የሚጠይቁት ጥያቄ ያለ ይመስለኛል፡፡ ለማነኛውም አቶ አባይ ፀሓዬ ከግላቸው አልፈው ህውሃትም ሆነ ፌዴራል መንግሰት አሁን በተፈጠረው ጉዳይ አያገባውም ጉዳዩ የኦህዴድ እና የኦህዴድ ሾሞች ብቻ ነው ብለው እጃቸውን ለመታጠብ ሞክረዋል፡፡ ይህ በፍፁም የሚሳካ አይመስለኝም፡፡

በእኛ አረዳዳ ኦህዴድ የሚባል ፍጡር በኢህአዴግ በሚመራው ስርዓት ውስጥ የተለይ ነው ብለን አናምንም፡፡ ኦህዴድ የወሰዳቸው የግል ውሳኔዎች አሉ ብለን አናምንም ስለዚህ ሁሉም የኢህአዴግ አመራር አባሎች እና የፌዴራል መንግሰቱ ባለስልጣናት በዚህ ውሳኔ ውስጥ እንዳሉበት እናምናለን፡፡ ሰለዚህም አሁን አቶ አባይ ፀሃዬ ያቀረቡት መከላከያ ተቀባይነት የለውም፡፡ እርሳቸው እንደሚሉት አንዳንዶቻችንም እንደምንስማማው የተቀናጀ ማስተር ፕላን በድፍኑ ክፋት የለውም፤ ክፋቱ የመጣው “በግድ ትተገብራላችሁ” የሚለው ማስፈራሪያ እና ጥቅም ካለው ማስገደድ እና ማስፈራራት ምን አመጣው? የሚለው እንደምታ ነው፡፡ ሰለዚህ ማርም ቢሆን በግድ ይመራል የምንለው!!!

በነገራችን ላይ ተጠያቂነት የሚባለው ነገር አቶ አባይ ፀኃዬ ከሃያ አራት ዓመት የስልጣን ዘመን በኋላም እንዴት ሊረዱት ተሳናቸው? ለምን ይህን የሚያክል ሀገራዊ ውሳኔ ወደ ወረዳና ዞን ሹሞች ሊወረውሩት ፈለጉ? ሌላው ደግሞ በኦሮሚያ አለ የሚሉት “መሬት መሸጥ፣ የመልካም አስተዳድር እጦት፣ ሙስና፣ ወዘተ እኛን አይመለከትም፡፡ ሕዝቡ የጠየቀው ትክክለኛ ጥያቄ ነው መልስ መስጠት ሲያቅታቸው አባይ፣ ሕውኃት፣ ፌዴራል” ይላሉ ብሎ ከሃላፊነት መሽሽ ይቻላል ወይ?ብለን መጠየቅ አለብን፡፡ በእኔ እምነት አሁንም ቢሆንም ማስተር ፕላኑ ተተግብሮ ውጤት ቢገኝ ጭብጨባውን ለመውሰድ ወደኋላ እንደማትሉት ሁሉ በዚህ መነሻ ለተነሱት መሰረታዊ የመልካም አስተዳድርና የነጻነት ጥያቄ መልስ መስጠት ካቃታችሁም ተጠያቂነቱንም አብራችሁ መሆን ይኖርበታል፡፡ በመጨረሻ አቶ አባይ ፀሃዬ የኦህዴድ የበታችና የመካከለኛ አመራር ላይ ክስ አቅርበዋል፡፡ እነዚህ የኦህዴድ አመራሮች በድርጅት መስመር ሄደው ይህ ክስ በይፋ ይነሳልን፣ ስናስፈፅም የነበረው ከፍተኛ አመራሩ የሰጠን መመሪያ ነው ማለት አለባቸው፡፡ ካለበለዚያ ደግሞ በጋራ ጥያቄያቸውን በኢህአዴግ ፎረም ላይ አቅርበው ሊገማገሙበት ይገባል፤ የአቶ አባይ የግል ከሆነም ግለ ሂስ እንዲያወርዱ ማድረግ አለባቸው፡፡ መቼም ኢህአዴግም ሆነ ኦህዴድ ስልጣን መልቀቅ ስለማይወዱ ብዬ ነው ከስልጣን ይውረዱ ያላልኩት፡፡ ስልጣኑን በግድ እስኪለቁ ግለ ሂስ ያውርዱ ለማለት ነው፡፡

ቸር ይገጠመን!!!

 

 

The post የአባይ ፀሃዬ የለውበትም የት ያደርስ ይሆን? – ግርማ ሰይፉ appeared first on Zehabesha Amharic.

የአማራ ብሔርተኝነት አስፈላጊነት በ-ብርሃኑ መልአክ

0
0

በቅድሚያ የአማራዊነት ትግል ያስፈለገው እንደሌሎቹ ብሄሩን በቅድሚያ የሚሰጥ አካል/ወያኔያዊ/ኦነጋዊ/ አመለካለቶች ጋር አብሮ ተዳብሎ ወይም ተደምሮ መታየት ያለበት አይመስለኝም ።

Displaced Amharas from West Shewa Aremya province Dec 2015

Displaced Amharas from West Shewa Aremya province Dec 2015

አዲሱ የአማራዊነትን ወገንተኝነት ሰሜት ያመጣው የከፋ የዘር መድልኦ ነው።ከላይ የጠቀስኳቸው ብሔሮች ከኢትዮጵያዊነት ይልቅ ብሄራቸው ቀድሞባቸው አማራውንም በዋነኛ ጠላትነት ፈርጀውት እየበሉት በመሆኑ ነው። አማራውን በመሳደብ እና በማንጓጠጥ እስከ ጥል ሃውልት በመስራት ከራሳቸው አልፈው እስከ ልጅ ልጆቻቸው የፀረ-አማራ እንቅስቃሴ ስለሚያደርጉ ነው።

አማራው ሃገሬ ብሎ ከሌሎች ብሄሮች ጋር በጋብቻ ተሳስሮ ከሚኖርበት ቀየው ንብረቱን ዘርፈው ሚስቱን እና ልጆቹን ደፍረው በገዛ ሃገሩ ስለ ገደሉት ነው።በአቀናው ሃገር ስላፈናቀሉት ነው።አማራ ስሄሆነ ብቻ ከነ ህይወቱ ገደል ውስጥ ስለወረወሩት ነው።

አማራ አማራነቴ ይቅደምብኝ ያለው የገዛ እርስተ – መሬቱን ዘርፈው ያልሆነ ማንነት በላዩ ላይ ጭነው በግድ ትግሬ ነህ ስላሉት ነው።የገዛ ርስተ- መሬቱን ነጥቀው ሚስቱን እንጀራ ጋጋሪ፤እሱን የቀን ሰራተኛ አድርገው የቁም ባርያ ስላደረጉት ነው። ከራስ ጥቅም ቅድምያ ከመስጠት አኳያ ሳይሆን አማራው እንደ አማራነቱ አንዳች ችግር ሌሌች ብሔረሰቦች ላይ እንደ ህዝብ ሳያደርስ ተዋልዶ በአንድነት ስም ሃገሩ ላይ ሲኖር በአገኙት አጋጣሚ የዘር ማጥፋት እየተደረገበት እንደ ሰው በሰላም መኖር ስላልቻለ ወደ ራሱ እያየ ነው።

መልሱም በሚገርም ሁኔታ ቀላል ነው።ይህ ሁሉ ግፍ እና ፍዳ እየደረሰበት አማራዊ ወገንተኝነት ስለሌለው ነው።በሌሎች ዘርን ያማከሉ አጉል ብሔርተኞች ተንኮል እና ደባ በመሆኑ እራሱን ለማዳን “አማራዊነትን” ወይም ቅድሚያ “እንደ አማራ” ተሰባስቦ ችግሩን መፍታት ስላለበት ነው።በአጉል ቅብጠት ወይም ትንሽነት ተሸብቦ ሌላው ማህበረሰብ ላይ አንዳች ጉዳት ለመፈፀም ፈልጎ አይደለም።

አማራው ላይ የሚፈፀመው ይህ ሁሉ ግፍ ፋሽስት ጣልያን ካመጣብን ግፍ የከፋ ቢሆን እንጅ አያንስም።

አማራው ቅድምያ እንደ “አማራ” ተሰባስቦ አንዳች መፍትሔ ካላመጣ ከእንደዚህ ካለ ከባድ መቅዘፍት ራሱን በምንም መንገድ ማዳን አይቻለውም።

አማራዊነት ማንነት ይለምልም!

የብሶቴ መሃል ወልቃይት ሆይ ብረሳሽ ቀኘ ይርሳኝ!
ብርሃኑ መልአክህ

The post የአማራ ብሔርተኝነት አስፈላጊነት በ-ብርሃኑ መልአክ appeared first on Zehabesha Amharic.


ሠበር ሰሚው ፍርድ ቤት በነ አቶ አያሌው ጉዳይ ላይ ሌላ ቀጠሮ ሰጠ

0
0

ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ለመስጠት ሲቀጥር ይህ ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑ ነው።

ሠበር-ሰሚው ፍርድ ቤት በቀድሞው የአንድነት ፓርቲ አመራር አባል በነ አቶ ሃብታሙ አያሌው እና ሌሎች ተከሳሾች ጉዳይ ላይ በመጪው ዓርብ ጥር 20 ቀን ውሳኔውን ለማሰማት ቀጠሮ ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ለመስጠት ሲቀጥር ይህ ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑ ነው።

መለስካቸው አምሃ ከአዲስ አበባ አጠናቅሮ ያዘጋጀውን ዘገባ ለማዳመጥ ይህንን ፋይል ይጫኑ።

The post ሠበር ሰሚው ፍርድ ቤት በነ አቶ አያሌው ጉዳይ ላይ ሌላ ቀጠሮ ሰጠ appeared first on Zehabesha Amharic.

የዕለቱ ምርጥ ካርቱን: ኦባማ እና ኃይለማርያም

ሀዋሳ ከመሬት መንቀጥቀጡ ሳታገግም አፍራሽ ግብረ ኃይል ተልኮ ገበያዋን እየናደው ነው

0
0

hawasa 2 hawasa 4 hawasa hawwasa 3

(በዳንኤል ፈይሳ)
≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈

በፖሊሶችና በነጋዴዎች መካከልም ግጭት ተቀስቅሶ ብዙ ሰዎች ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን የተወሰኑ ነጋዴዎችም ታፍሰው ታስረዋል።

ከሰሞኑ በርዕደ መሬት ለአምስት ጊዜ ያህል የተመታችው ሀዋሳ ከተማ ከአስደንጋጩ ሁኔታ ሳታገግም ሰፊው ገበያዋ ደግሞ በአፍራሽ ግብረ ኃይል መናድ ጀምሮዋል።

አረብ ሰፈር በተለምዶ አሮጌ ገበያ የሚባለው ቦታ ላይ ለረጅም አመታት እየነገዱ ራስቸውንና ቤተሰባቸውን ያስተዳድሩ የነበሩ ከ200 በላይ የሚሆኑ ነጋዴዎች የንግድ ቦታቸው ከትላንትና አመሻሽ ጀምሮ በዛሬው እለት ቀጥሎ እንዳልነበር ሆኖ ወዳድሞዋል።

ለማፍረስ እንደ ምክንያት የሚጠቅሱት ሌላምግዜ እንደሚሉት የከተማ ወበትና ህገወጥ የቤቶች ግንባታ ነው ነጋዴዎቹና አገልግሎት ሰጨዎቹ በሸራ በብረትና በጣውላየከለሉዋቸውን ቦታዎች መጠቀም ላልቻሉ እቃዎቻቸውበዝናብና በጸሃይ በመጎዳት ይበላሽባቸዋል በዚህም ምክኒያት እጅግ የከፋ ኪሳራና ጉዳት ደርሶባቸዋል ። ነጋዴዎቹ ሙሉ በሙሉ የቫትና ቲኦቲ ህጋዊ ግብር ከፋዮች ናቸው።

በገበያው በጣም ውጥረት ነግሷል ዳሶቹንየማፍረስ ስራው ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሏል በነጋዴዎቹናበፖሊሶች መሃል ግጭት ተነስቶ ብዙ ሰዎች ተጎደተዋልተቃውሞ ለማሰነሳት የሞከሩትን ሰዎች ሱቃቸውን በማሸግወደ ፖሊስ ጣቢያ አግዘዋቸዋል በመሃል መሰረቱ የተናጋ አንድ
ቤት ተደርምሶ በ አንድ ባጃጅና አንደ ሰው ላይ ከፈተኛ ጉዳትደርሷል የአካባቢው ገጽታ ሙሉ በሙሉ ማለት ይቻላልተቀይሯል በተፈጠረው ግር ግር የንግድ አገልግሎቱ ለግዜው
ተቋርጧል ።

The post ሀዋሳ ከመሬት መንቀጥቀጡ ሳታገግም አፍራሽ ግብረ ኃይል ተልኮ ገበያዋን እየናደው ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

ሚኒሶታና ኢትዮጵያ ያጣቻቸው ታላቅ ሰው የአቶ ታዬ ረታ የለቅሶ እና የቀብር ሁኔታ መረጃዎች |በተለይ ለሚኒሶታ ነዋሪዎች

0
0
አቶ ታዬ ረታ በፍኖተ ጥበብ ማዕከል የዓመቱ ምርጥ ሰው በሚል ሽልማት በተቀበሉበት ወቅት በዘ-ሐበሻ አዘጋጅ የ እጅ ስልክ የተነሱት ፎቶ::

አቶ ታዬ ረታ በፍኖተ ጥበብ ማዕከል የዓመቱ ምርጥ ሰው በሚል ሽልማት በተቀበሉበት ወቅት በዘ-ሐበሻ አዘጋጅ የ እጅ ስልክ የተነሱት ፎቶ::

(ዘ-ሐበሻ) ትናንት ዘ-ሐበሻ የታላቁን ሰው አቶ ታዬ ረታ ህልፈተ ሕይወት መዘገቧ አይዘነጋም:: ቃል በገባነው መሰረት ለቅሶ መድረስ ለሚፈልጉ እንዲሁም በቀብራቸው ላይ ለመገኘት ለሚሹ ከቤተሰቦቻቸው መረጃዎችን ጠይቀን ይዘን መጥተናል::

ለቅሶ መድረስ ለሚፈልጉ ነገ ሐሙስ እና አርብ ከቀኑ 2:00 ሰዓት ጀምሮ በላዖ ኮምዩኒቲ ሴንተር በመምጣት ቤተሰቦቻቸውን እና ወዳጆቻቸውን ማግኘት ይቻላል::

ለቅሶ የሚደረስበት የላዖ ኮምዩኒቲ አድራሻ:-

Lao Family Community Of Minnesota
Address: 320 University Ave W, St Paul, MN 55103

የፍትሃት ሰነስርዓት የፊታችን ቅዳሜ ጃንዋሪ 30, 2016 ዓ.ም በደብረሰላም መድሃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከ10 ሰዓት እስከ 12 ሰዓት ድረስ ይካሄዳል::

ፍትሃት የሚደረግበት ቦታ አድራሻ:-
Debre Selam Medhanealem Ethiopian Orthodox Tewahedo Church
Address: 4401 Minnehaha Ave, Minneapolis, MN 55406

እንዲሁም የፊታችን ቅዳሜ የፍትሃት ስነሥርዓቱ በደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤተክርስቲያን እስከ 12 ሰዓት ከተደረገ በኋላ አስከሬናቸው የሚያርፍበት የቀብር ሥፍራ አድራሻ የሚከተለው ነው::

Hillside Funeral Chapel
2600 19th Ave NE, Minneapolis, MN 55418

በተጨማሪም ከቀብር በኋላ በላዖ ኮምዩኒቲ የስንብት መርሃ ግብር ተዘጋጅቷል::

ገጣሚ ፍሰሃ ሃይሉ ስለአቶ ታዬ እረፍት የሚከተለውን አጭር ስንኝ ቋጥሯል::

 

ታዬ ረታ ተረታ!

ሞትን አሸንፎ ካንድም አስር ጊዜ፣
ዛሬ ግን ተ―ረታ፣ ሄደ ሳይል ጓዜ፣
በመለየት ድባብ በናፍቆት አባዜ፣
ታየ “በቃ” ብሎ ጣለብን ትካዜ።

The post ሚኒሶታና ኢትዮጵያ ያጣቻቸው ታላቅ ሰው የአቶ ታዬ ረታ የለቅሶ እና የቀብር ሁኔታ መረጃዎች | በተለይ ለሚኒሶታ ነዋሪዎች appeared first on Zehabesha Amharic.

አቶ ታየ፥ እባክህ አሁንም እንደ ሌላው ጊዜ ተነሣ |ጌታቸው ኃይሌ

0
0

Taye Reta

“ሞት ሁል ጊዜ እንግዳ ነው” ይባላል። ለአቶ ታየ ግን እንግዳ አልነበረም። ስልክ ስንደዋወል ጨዋታችንን የምንጀምረው “ትናንት ሞቼ ተነሣሁ” ብሎኝ ነው። እሱ ካልነገረኝም፥ “ዛሬ አልሞትክም ነበር ወይ” ብየ እጠይቀው ነበር። እንደሰማሁት፥ አሁንም ወደዘላለማዊ ዓለም የሄደው ከሞተበት ተነሥቶ አጠገቡ ለመገኘት ዕድል ያገኙትን ተሰናብቶ ነው። አቶ ታየ፤ እባክህ አሁንም እንደ ሌላው ጊዜ ተነሣ። ሌላው ቢቀር የቱን ያህል ሕዝብ ከምን ያህል ሐዘን ላይ እንደጣልከው አይተህ አንቀላፋ።

አቶ ታየ የሀገር ቅርስ ስለነበረ፥ የሱ ከዚህ ዓለም መለየት የሚያሳዝነው የቅርብ ዘመዶቹን ብቻ አይደለም። የሚፈሰው ዕንባ መሬት ያረጥባል። ዜናው አንጀት ያላውሳል፤ ልብ ያደክማል፤ የአእሞሮን በትክክል የማሰብ ችሎታ ያሳንሳል፤ እጅ እግር ይዝላሉ። የሐዘን እንጉርጉሮ ይጐርፍለታል። ድርሰት የመድረስ ችሎታ የሌለው ለመጀመሪያ ጊዜ ሲቆጭ ይታያል። እንደ አቶ ታየ ያለ የታሪክ ሰው ሲሞት ስሕተቶች ቢኖሩት አብረው ይቀበሩና አስተዋፅኦዎቹ ሲያብቡ ይኖራሉ። አቶ ታየ ከሙታኑም ከሕያዋኑም ጋር አብሮ የሚኖር የታሪክ ሰው ነው።

አቶ ታየ አቻ ጓደኛየ ስለነበረ የሄደው በእኔና በሱ መካከል ያለውን የጓደኞች የውይይት ምዕራፍ ዘግቶ ነው። ከእሱ ጋር የማወራቸውን ጨዋታዎችና ቀልዶች ከማንም ሌላ ሰው ፊት አላነሣቸውም። ጥንት “የካምፖ ሎጆ” ጓደኞች ነበርን። ደርግ ማስመሰል እንኳ ስለማያውቅ ሳይሳካልን ቀረ እንጂ፥ የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት እንደወደቀ ፓርቲ ልናቋቁም ከታየ ጋር አምስት ሆነን በሳምን አንድ ቀን አንዳችን ቤት እየተገናኘን እንወያይ ነበር።
አቶ ታየ ሁል ጊዜ የተሻለ ዘመን እንደሚመጣ ስለሚያምን፥ ምንም ነገር የማያስደነግጠው ጀግና ነበረ። አንዳንድ በሕይወቱ የደረሱበትን አስጊ ነገሮች ሲያጫውተኝ፥ “ይኸ ነገር በእኔ ላይ ደርሶ ቢሆን የምይዘውና የምጥለው ይጠፋኝ ነበር” ስለው ይሥቅ ነበር። አቶ ታየ ያረፈው የማረፍ ፍርሀትና ሥጋት ሳይነኩት ነው።

እንዳየሁት አንዱ የአቶ ታየ የብርታት ምንጭ ከባለቤቱ፥ ከልጆቹና ከእኅቶቹ የሚደርሰው ወሰን አልባ ፍቅር ነው። አጠገቡ ላሉ ኢትዮጵያውያን ክቡር አቶ ታየ እና ጋሸ ታየ ሲሆን፥ ለእኅቶቹ ጋሽዬ ነበር።ከአቶ ታየ ጋር ጥቂት ጊዜ አብሮ የሚቆይ ሰው ታሪክ ተምሮ የሕይወት ምሥጢር ተገልጾለት ይሄዳል። አሁን እንግዴህ ያለ ታየ መኖርን ልንማር ነው። ትምህርቱ እንዲስማማን አምላካችንን እንለምነዋለን።

አቶ ታየ ንጹሕ ሕይወት ስለ ኖረ፤ ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው፥ “አምላክ ዓይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልቦና ያልታሰበውን ቅዱስ ስሙን ለሚወዱ ያዘገጀውን” ያውርስልን። ከአባቶቻችን ከአብርሃም፥ ከተክለ ሃይማኖት፥ ከኢየሱስ ሞአ፥ ከኤዎስጣቴዎስ ጋራ ለዘላለም ያኑርልን።
ሐዘንተኞች ሁሉ፥ በተለይም ቤተ ሰቦቹ፥ ባለቤቱ፥ ልጆቹና እኅቶቹ እግዚአብሔር ያጽናችሁ።

The post አቶ ታየ፥ እባክህ አሁንም እንደ ሌላው ጊዜ ተነሣ | ጌታቸው ኃይሌ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live