Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

አቶ እውነቱ ብላታ የሥልጣን ዕድገት አገኙ

0
0

እውነቱ ብላታየኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ዳይሬክተር የነበሩት አቶ እውነቱ ብላታ ደበላ ከያዙት ኃላፊነት ተነስተው ከፍ ወዳለው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው መሾማቸውን ሰንደቅ ጋዜጣ ከአዲስ አበባ ዘገበ። እንደጋዜጣው ዘገባ አቶ እውነቱ የተሾሙት ቦታ አቶ በከር ሻሌ በአሁኑ ወቅት የገቢዎችና ጉምሩክ ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙት የያዙት ቦታ ሲሆን አቶ በከር ከዚህ ኃላፊነታቸው ተነስተው የአዳማ ከንቲባ ሆነው ከተሾሙ በኋላም ከዘጠኝ ወራት በላይ ቦታው ክፍት ሆኖ መቆየቱ ታውቋል።
ጋዜጣው ዘገባውን ቀጥሎ አቶ እውነቱ ብላታ ቀደም ሲል በኦሮሚያ ክልል የፍትህና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ሆነው የሰሩ ሲሆን በኋላም በፌዴራል ጉዳዮች ጽ/ቤት በከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ ሲሰሩ ከቆዩ በኋላ በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን ተሹመው ለአንድ ዓመት ሲሰሩ ቆይተዋል ብሏል።


የድምፃዊ ኢዮብ መኮንን የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ይፈፀማል

0
0

በአሸናፊ ደምሴeyob
ሰንደቅ ጋዜጣ እንደዘገበው በሬጌ የሙዚቃ ስልት አጨዋወቱ በበርካቶች ዘንድ አድናቆትን ያተረፈው ድምጻዊ እዮብ መኮንን ባሳለፍነው ቅዳሜ ለህክምና በሄደበት ኬኒያ ናይሮቢ ውስጥ በሚገኝ አጋ-ካሃን የተሰኘ ሆስፒታል ህይወቱ ማለፉን ተከትሎ ትናንት ማምሻውን ወደሀገሩ የተመለሰው አስክሬኑ፤ ዛሬ ከቀኑ በ9ሰዓት በቅዱስ ስላሴ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቀብሩ እንደሚፈፀም ምንጮች አስታወቁ።
“እንደቃል” በተሰኘው ብቸኛና የመጀመሪያ አልበሙ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አትርፎ የነበረው ድምፃዊ እዮብ፤ ባሳለፍነው ሳምንት ማክሰኞ ዕለት የእህቱን ልጅ ትምህርት ቤት አስመዝግቦ ከተመለሰ በኋላ የግቢውን በር በማንኳኳት ላይ ሳለ ራሱን ስቶ መውደቁ የታወቀ ሲሆን፤ ህመሙም የጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ (stroke) መሆኑ ታውቋል።
ከድንገተኛ አደጋው በኋላ ራሱን ስቷል። በቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል የህክምና እርዳታውን ሲያገኝ የቆየው ድምፃዊው፤ ለተሻለ የህክምና እርዳታ ወደኬኒያ፤ ናይሮቢ አምቡላንስ ባለው የግል አውሮፕላን ቅዳሜ ምሽት ከሀገሩ የወጣው እዮብ ጤናውን ይዞ መመለስ ሳይችል ቀርቷል።
በኬኒያ የሚገኙ የህክምና ባለሙያዎች የወጣቱን ድምጻዊ ህይወት ለመታደግ የተቻላቸውን የጣሩ ቢሆንም፤ ድምጻዊ እዮብ መኮንን ግን በተወለደ በ38 ዓመቱ እሁድ ነሐሴ 12 ቀን 2005 ዓ.ም ምሽት 3፡45 አካባቢ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።
ድምጻዊው ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት ሲሆን፤”እንደቃል” በተሰኘው ተወዳጅ አልበሙ በተጨማሪም በቅርቡ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቅ የሙዚቃ ስራውን ከ70 በመቶ በላይ አጠናቆ እንደነበር ምንጮች ይጠቁማሉ።

ሰማያዊ ፓርቲ በመብራት ኃይል አዳራሽና በምኒልክ ት/ቤት ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳላደርግ በቢሮክራሲያዊ መንገድ ተከለከልኩ አለ

0
0

semayawi parti
(ዘ-ሐበሻ) ከዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ዝምታን ሰብሮ አደባባይ በመውጣት ስም ያተረፈው ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኙት የመብራት ኃይል አዳራሽና በምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አዳራሾች ውስጥ ሕዝባዊ ስብሰባ ለማካሄድ ባቅድም በቢሮክራሲያዊ መንገድ ተከለከልኩ አለ።
ሰማያዊ ፓርቲ በፌስቡክ ገጹ “በቃል እንጂ በተግባር የማይታየው ህገ-መንግስታዊ መብት” በሚል በበተነው መረጃ ነሀሴ 19 ቀን 2ዐዐ5 ዓ/ም. በመብራት ሀይል አዳራሽ በሰማያዊ ፓርቲ ሊካሄድ ታስቦ የነበረው ሕዝባዊ ስብሰባ በተለመደው የመንግሥት ቢሮክራሲና አፈና ተደናቀፈ ብሏል፡፡ ይኸውም የአዳራሹ ባለቤት የሆነው የኢ.መ.ኃ.ባ. ስብሰባው በአስተዳደሩ እውቅና ያለው መሆኑን የሚገልፅ ደብዳቤ ሲጠይቅ የአ.አ. መስተዳድር ደግሞ አዳራሹን እንድትከራዩ ባለስልጣን መ/ቤቱ የፈቀደላችሁ መሆኑን የሚገልፅ ደብዳቤ አምጡ በሚል ውስጣዊ መነጋገር ባለበት ግልፅ ቢሮክራሲ ስብሰባው እንዳይደረግ መሰናክል ፈጥሯል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰማያዊ ፓርቲ ነሀሴ 26 ቀን እንዲካሄድ ኘሮግራም የያዘለትን ሁለተኛ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ዝግጅት በተጠናከረ ሁኔታ ቀጥሏል፡፡ በዛሬው እለትም ለአ.አ. መስተዳድር የሰላማዊ ሰልፍና ህዝባዊ ስብሰባ ማሣወቂያ ክፍል የማሣወቂያ ደብዳቤውን ያስገባ ሲሆን ይህ ክፍል ግን የእውቅና ደብዳቤውን ለመቀበል ፈቃደኛ ባይሆንም እንደተለመደው ደብዳቤውን በብዙ ምስክሮች ፊት በማሳወቂያ ክፍል ኦፊሠሩ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠው መጥተዋል፡፡
በሌላ በኩል የፓርቲው የህግ ጉዳይ ኃላፊ ወጣት ይድነቃቸው ከበደ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፀው ፓርቲው በመጪው እሁድ በመብራት ኃይል አዳራሽና በምኒልክ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አዳራሽ ጥያቄ አቅርቦ የአዳራሾቹ ባለቤቶች ፓርቲው ስብሰባ ለማካሄድ ከአዲስ አበባ አስተዳደር የፈቃድ ደብዳቤ እንዲያመጣ ሲጠይቁ የአዲስ አበባ አስተዳደር በበኩሉ ለአዳራሽ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ አምጡ በማለቱ ቢሮክራሲያዊ በሆነ መንገድ አዳራሾቹን መከልከሉን ተናግረዋል።
“ወደ አዳራሾቹ ባለቤት ሄደን ክፍያ ልንፈፅም ስንል ፈቃድ አምጡ ይሉናል። ከአዲስ አበባ አስተዳደር ደግሞ ፈቃድ ስንጠይቅ የተዋዋላችሁበትን ደረሰኝ አምጡ በማለት አጉላልተውናል” ያለው ወጣት ይድነቃቸው በግል የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ የሆኑትን አቶ አባተ ስጦታውን ቢያናግሩም ፈቃዱ ሊሳካ አልቻለም ብሏል።
በተያያዘ ፓርቲው ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የእውቅና ደብዳቤ ማስገባቱንና ሰልፉን ሊያደምቁ የሚችሉ ልዩ ልዩ ቅድመ ዝግጅቶች እያካሄዱ መሆኑን ከወጣት ይድነቃቸው ገለፃ መረዳት ተችሏል።
በሌላ በኩል ፓርቲው ቀበና በሚገኘው ጽ/ቤቱ በየሳምንቱ እሁድ ምሁራንን እየጋበዘ የሚያደርገውን ውይይት በመቀጠል በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መምህር የሆኑትን ዶ/ር በቃሉ አጥናፉ ታዬን በመጋበዝ “የግጭት አፈታት በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ በቀጣይ እሁድ ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ ፓርቲው ለተለያዩ ሚድያዎች በላከው መግለጫ ላይ አስታውቋል። ጋዜጣው በዘገባው ማጠናቀቂያ ላይ እንዳለው ዶ/ር በቃሉ በአሁኑ ወቅት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር ሲሆኑ በሳይኮሎጂና በእንግሊዝኛ ቋንቋ ሁለት ማስተርስ ዲግሪ ያላቸው ሲሆን በትምህርት (Education) የመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በቋንቋና ስነልቦና የፒኤች ዲግሪ አላቸው። ከአስር ዓመት በላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በማስተማር ላይ ይገኛሉ።

ወ/ሮ ሃዲያ መሀመድ ከ18 ቀን እስር በኋላ በ10ሺህ ብር ዋስ ተለቀዋል

0
0

ፍኖተ ነፃነት

የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን አመራር የሆኑት ወ/ሮ ሃዲያመሀመድ ከ18 ቀን እስር በኋላ በ10,000 ብር ዋስ ተለቀዋል፡፡ አንድት በወላይታ ሶዶ  ሐምሌ 28 ቀን 2005 ዓ.ም ያካሄደው ህዝባዊ ስብሰባ እንዲጨናገፍ የተለያዩ የውንብድና ድርጊቶችን ሲፈፅም የነበረው የዞኑ የዞኑ አስተዳደር ወ/ሮ ሃዲያ መሀመድን  “አንድነት ፓርቲ ሙስሊሙን ህብረተሰብ ለአመፅ የሚቀሰቅስ በራሪ ወረቀት እንድበትን ተልዕኮ ሰጥቶኛል” ብለው እንዲመሰክሩ ጫና ቢያደርግባቸውም ባለመስማማታቸው ለ18 ቀናት በእስር እንዲማቅቁ አድርጓቸዋል፡፡

*ፎቶዎቹ ወ/ሮ ሃዲያ መሀመድ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት የተነሱ ናቸው፡፡

1187226

1001722_1174670_

የአቶ መለስ የሙት ዓመት ልዩ ዝግጅት (ESAT efeta 21 August 2013)

ሃይማኖትና ፖለቲካ በኢትዮጵያ –ከዶ /ር ብርሃኑ ነጋ

0
0

Dr. Birhanu Nega

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

1. መግቢያ:

ካለፈው ሁለት አመት ግድም ጀምሮ “መንግሥት በዲናችን ጣልቃ አይግባብን” በሚል ሰፊ ማእቀፍ ውስጥ በሰላማዊ መንገድ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እየተደረገ ያለው ትግል፤ በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ደግሞ ሁለት አስርት አመታትን ያስቆጠረ ከቀኖናው ውጭ መንግሥት የቤተክርስቲያኑን መሪ አይምረጥብን በሚል በመሰረታዊ ሀሳቡ ከሙስሊሙ ጥያቄ ጋር ተመሳሳይ በሆነ ጉዳይ በተነሳ ውዝግብ ቤተክርስቲያኒቱ ለሁለት ተከፍላ ያለችበት ሁኔታና በዚህም ምክንያት በመንግሥት የተገፋው “ስደተኛው ሲኖዶስ” በራሱ ላይ የደረሰውን ሁከት በመቃወም የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ተዳምረው ምናልባት ለመጀመሪያ ጊዜ ጤነኛ የሆነው የሀይማኖትና የፖለቲካ ግንኙነት ምንድን ነው? ወይንም ደግሞ የመንግሥትና የሀይማኖት ግንኙነት ምን መሆን አለበት? የሚለውን ጥያቄ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው የሀይማኖቱ ተከታዮች አልፎ ያጠቃላይ የፖለቲካ ማህበረሰቡ (የሀገሩ) ትልቅ የመወያያ አርዕስት እየሆነ ነው:: ይህ ጉዳይ ግን ጥቅል ከሆነ ያመለካከትና የንድፈ ሀሳብ ጥያቄ በተጨማሪ ጥልቅና አስቸኳይ የሆነ የተግባር ፖለቲካ ጥያቄም ነው ይዞ የመጣው::

ሙሉውን ጽሑፍ በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

 

 

ሃይማኖትና ፖለቲካ በኢትዮጵያ –ከዶ /ር ብርሃኑ ነጋ

0
0

Dr. Birhanu Negaከዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

1. መግቢያ:

ካለፈው ሁለት አመት ግድም ጀምሮ “መንግሥት በዲናችን ጣልቃ አይግባብን” በሚል ሰፊ ማእቀፍ ውስጥ በሰላማዊ መንገድ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እየተደረገ ያለው ትግል፤ በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ደግሞ ሁለት አስርት አመታትን ያስቆጠረ ከቀኖናው ውጭ መንግሥት የቤተክርስቲያኑን መሪ አይምረጥብን በሚል በመሰረታዊ ሀሳቡ ከሙስሊሙ ጥያቄ ጋር ተመሳሳይ በሆነ ጉዳይ በተነሳ ውዝግብ ቤተክርስቲያኒቱ ለሁለት ተከፍላ ያለችበት ሁኔታና በዚህም ምክንያት በመንግሥት የተገፋው “ስደተኛው ሲኖዶስ” በራሱ ላይ የደረሰውን ሁከት በመቃወም የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ተዳምረው ምናልባት ለመጀመሪያ ጊዜ ጤነኛ የሆነው የሀይማኖትና የፖለቲካ ግንኙነት ምንድን ነው? ወይንም ደግሞ የመንግሥትና የሀይማኖት ግንኙነት ምን መሆን አለበት? የሚለውን ጥያቄ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው የሀይማኖቱ ተከታዮች አልፎ ያጠቃላይ የፖለቲካ ማህበረሰቡ (የሀገሩ) ትልቅ የመወያያ አርዕስት እየሆነ ነው:: ይህ ጉዳይ ግን ጥቅል ከሆነ ያመለካከትና የንድፈ ሀሳብ ጥያቄ በተጨማሪ ጥልቅና አስቸኳይ የሆነ የተግባር ፖለቲካ ጥያቄም ነው ይዞ የመጣው::

ሙሉውን ጽሑፍ በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

 

 

ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 54 (PDF)


የኢዮብ መኮንን የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ

0
0

eyob mekonen 1

eyob mekonen 2(ዘ-ሐበሻ) በሬጌ የሙዚቃ ስልት አጨዋወቱ በበርካቶች ዘንድ አድናቆትን ያተረፈው ድምጻዊ እዮብ መኮንን ባሳለፍነው ቅዳሜ ለህክምና በሄደበት ኬኒያ ናይሮቢ ውስጥ በሚገኝ አጋ-ካሃን የተሰኘ ሆስፒታል ህይወቱ ማለፉን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ ይታወሳል። በዚህም መሠረት ዛሬ ከቀኑ በ9ሰዓት በቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቀብሩ በርከት ያሉ አድናቂዎቹ፣ የሙያ አጋሮቹ እና ቤተሰቦቹ በተገኙበት ተፈጽሟል።
“እንደቃል” በተሰኘው ብቸኛና የመጀመሪያ አልበሙ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አትርፎ የነበረው ድምፃዊ እዮብ፤ ባሳለፍነው ሳምንት ማክሰኞ ዕለት የእህቱን ልጅ ትምህርት ቤት አስመዝግቦ ከተመለሰ በኋላ የግቢውን በር በማንኳኳት ላይ ሳለ ራሱን ስቶ መውደቁና በዚህ የተነሳም በተገኘበት ስትሮክ ለሞት እንደበቃ በዘ-ሐበሻ በተደጋጋሚ ከታመመበት ጊዜ ጀምሮ ሲዘገብ ሰንብቷል። የጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ (stroke) መሆኑ ታውቋል።
በተወለደ በ38 ዓመቱ እሁድ ነሐሴ 12 ቀን 2005 ዓ.ም ምሽት 3፡45 አካባቢ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ድምፃዊው ድምጻዊው ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት ነበር። በተጨማሪም በቅርቡ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቅ የሙዚቃ ስራውን ከ70 በመቶ በላይ አጠናቆ እንደነበር በተለያዩ ሚድያዎች የተዘገበ ሲሆን ለድምፃዊው መታሰቢያ ይሆን ዘንድ የተጠናቀቁትን ሙዚቃዎች ለማሳተም እቅድ እንዳለም ለዘ-ሐበሻ ከደረሰው መረጃ መረዳት ተችሏል።

Sport: የጎደለው ሊቨርፑል

0
0

ብሬንዳን ሮጀርስ በሊቨርፑል ባሳለፉት የመጀመሪያው ዓመታት ደጋግመው የሚሰነዝሩት አስተያየት ነበር፡፡ ‹‹እንደ ቡድን በመከላከል ረገድ መሻሻል ይገባናል›› ይሉ ነበር፡፡ ‹‹እንደ ቡድን›› የሚለው ቃል መላው ቡድኑን የሚወክል አይደለም፡፡ የተከላካዩን መስመር ብቻ ለመጥቀስ ፈልገው ነው፡፡ ባሳለፍነው የውድድር ዘመን ሮጀርስ ሊቨርፑል ከኋላ ኳስ እየመሰረተ እንዲጫወት ለማድረግ ጥረዋል፡፡ አሰልጣኙ ማየት የሚፈልጉትን የጨዋታ ዘይቤ ቡድኑ የመጫወቱ ነገር ሙሉ ለሙሉ ባይባልም ምልክቶችን አሳይቷል፡፡ እያደርም መሻሻል ተስተውሎበታል፡፡ የመከላከል ስህተቶች የቡድኑን መልካም ስራ አፈር ሲያለብስ ታይቷል፡፡ ከሁሉም በላይ ማርቲን ስከርትል ጥያቄ ውስጥ ገብቷል፡፡
suarez
ስሎቫኪያዊው የመሀል ተከላካይ በ2011/12 የሊቨርፑል ኮከብ ተጨዋች ተብሎ ተመርጦ ነበር፡፡ ባሳለፍነው የውድድር ዘመን በሊቨርፑል ሁለተኛ ጨዋታ ላይ ወደኋላ ያቀበላት ኳስ ያስከፈላቸው ዋጋ የዓመቱ ችግሩ መነሻ ሆናለች፡፡ ሮጀርስ ኳስ ከኋላ ጀምሮ እንዲመሰረት መፈለጋቸው ለስከርትል መልካም አልሆነም፡፡ የአስቶንቪላው ክሪስቲያን ቤንቴኬ በአንፊልድ በሊቨርፑል ተከላካይ መስመር ላይ ሲረማመድ ግን የማስጠንቀቂያው ደውል ይበልጥ ጮኸ፡፡
ሮጀርስ ቡድኑ የበለጠ እስኪጎዳ ድረስ መጠበቅ አልነበረባቸውም፡፡ ችግሩን ለማቃለል በወሰዱት እርምጃ ስከርትልን ወደ ተጠባባቂነት አወረዱት፡፡ በምትኩም አንጋፋውን ጄሚ ካራገርን ወደ ቋሚው አሰላለፍ መለሱት፡፡ ከውሳኔው በኋላ ስከርትል የቋሚነት ዕድል ያገኘው ከትንሹ አልድሃም ጋር ባደረጉት ጨዋታ ነበር፡፡ በማንኛውም ሰዓት ከባድ ስህተት ሊፈፀም የሚችል የመሰለው የተከላካይ መስመር በካራገር መመለስ ቢያንስ በመሪነት ችሎታው ተጠቀመ፡፡ ሆኖም ካራ ፍጥነት ያለው ተጨዋች ባለመሆኑ ሮጀርስ ለሚፈልጉት ወደፊት መጥቶ የመከላከል ዘዴ አይሆንም፡፡ ከበስተኋላው ሰፊ ክፍተት ትቶ ወደ ፊት የሚገፋ ተከላካይ መስመር ከተጣሰ የመሀል ተከላካዩ ፈጣን ካልሆነ ጉዳቱ ብዙ ነው፡፡ እናም የሮጀርስ ወጥቶ የመከላከል ዘዴ ተግባራዊ ለማድረግ አስቸጋሪ ሆነ፡፡ ከአዲሱ ዓመት መግባት በኋላ ግን ሊቨርፑል በመልሶ ማጥቃት ወደ ሚጫወት ጠንካራ ቡድንነት ተቀየረ፡፡ በዚያው ጊዜ በአንፊልድ ምርጥ ጨዋታዎችን ማሳየት ጀመረ፡፡ ሆኖም ካራገር በውድድሩ ዘመን ማብቂያ ላይ ከተጫዋችነት ለመገለል መወሰኑ ለሮጀርስ ራስ ምታት ይዞ መጣ፡፡ አሰልጣኙም የኋላ መስመራቸውን ሙሉ ለሙሉ ለመቀየር ግዴታ ውስጥ ገቡ፡፡
የሊቨርፑል ተከላካይ ድክመት በመሀል ብቻ አልነበረም፡፡ የሆዜ ኤንሪኬ ብቃት ቀባይነት ይጎድለዋል፡፡ ብቃቱ ሲመጣለት አስደናቂ ጨዋታን ያሳያል፡፡ ሆኖም የተመልካቹን ቆሽት የሚያሳርርባቸውን ጨዋታዎች ጥቂት አልነበሩም፡፡ በማጥቃቱ ደጋፊውን ተስፋ ያስቆርጣል፡፡ በራሪ የክንፍ ተጨዋቾች በተቃራኒው ሲገጥሙት ደግሞ በመከላከሉ ረገድ ተብረክርኮ ይቀራል፡፡
በተቃራኒው መስመር ብንመለከት እንደግሌን ጆንሰን የሚያጠቁ ፉልባኮች ብዙ አይደሉም፡፡ ሲከላከል ካለፉት ጊዜያት የበለጠ ብቃት ነበረው፡፡ ሆኖም ስቴዋርት ዳውኒንግን በግራ መስመር ተከላካይነት በማሰለፍ አሮን ሌነንን ማጋፈጥ ከባድ ስህተት ይሆናል፡፡
በ2012/13 ሊቨርፑል 43 ጎሎች ተቆጥረውበታል፡፡ ቀደም ባለው ዓመት ደግሞ 40 ጊዜ መረቡ ተደፍሯል፡፡ የቻምፒየንስ ሊግ ቦታን እንዳያገኝ ዋነኛ እንቅፋት የፈጠረበት ተከላካዮች በግል የሚፈፅሟቸው ስህተቶች ናቸው፡፡
የዳንኤል አገር እና የስከርትል ጥምረት በውድድር ዘመኑ የመጀመሪያ ጫዋዎች ላይ ሊመለስ ይችላል፡፡ በፕሪሚየር ሊጉ ኳስን መጫወት ከሚችሉ የመሀል ተከላካዮች ግንባር ቀደሙ ዳንኤል አገር ነው፡፡ ባለፈው ውድድር ዘመን ከአገር የበለጠ ጨዋታ የተጫወቱት የሊቨርፑል ተጨዋቾች ስቲቭን ዤራርድ እና ግሌን ጆንሰን ብቻ ናቸውው፡ አገር ምን ያህል የማይዋዥቅ ብቃት እንደነበረው ይህ መረጃ ጠቋሚ ነው፡፡ በ2011 ስከርትል ከዚህ ዴንማርካዊ ጋር ልዩ ጥምረትን በመፍጠር ከፍ ሲልም ለተከላካይ መስመር እንደ ቡድን መዋሃድ ምክንያት ሆነው ነበር፡፡ ስከርትል ኳስን በእግሩ ይዞ የአገር ያህል ችሎታ ባይኖረውም ሰፋ ያለ ርቀት መሸፈን የሚችልና ተንቀሳቃሽ ነው፡፡ ጠንካራ ጎኑን ለመጠቀም መቻሉ በራሱ ልዩ ችሎታ ነው፡፡ ሆኖም የማት ስሚዝ መጫወቻ ሲሆን ማየት ደጋፊውን የሚያስደስት አይደለም፡፡ ድክመቱ በራስ መተማመን ችግር ይምጣ ወይም በችሎታ ማነስ ይከሰት መልሱ ያከራክራል፡፡ ይሁን እንጂ በሊቨርፑል ከቆየ በሮጀርስ የብቃት ትንሳኤ ማግኘቱ የማይቀር ይመስላል፡፡
ኮሎ ቱሬ የመጪው የውድድር ዘመን አማራጭ የመሀል ተከላካይ ይሆናል፡፡ ቱሬ ከአገር ጋር ሊጣመር ይችላል፡፡ ኮሎ ከሁለት የተለያዩ ክለቦች ጋር ሊጉን ማሸነፍ ከቻሉ ጥቂት ተጨዋቾች አንዱ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ እንዲሁም የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን ከሆኑ በኋላ ለሊቨርፑል ከተጫወቱ እጅግ ጥቂት ተጨዋቾች አንዱ ነው፡፡ ሮጀርስ የሚፈልጉትን ‹‹የማሸነፍ ስነ ልቦና›› ከራሱ ጋር ይዞ ወደ ቡድኑ መጥቷል፡፡ ከአገር የአየር ላይ የመከላከል ብቃት ጋር የተሟላ ጥምረት ለመፍጠር ያስችላል፡፡ ቱሬ አርሰናል አንድም ጨዋታ ሳይሸነፍ ሻምፒዮን ከሆነበት ዘመን የነበረው ፍጥነት እምብዛም አልቀነሰም፡፡ ባለፉት ሁለት የውድድር ዘመናት በሮቤርቶ ማንቺኒ ተጠባባቂ መደረጉ አሁን ራሱን ብቁ መሆኑን ለማሳየት እንዲነሳሳ ያደርገዋል፡፡
በቀኝ ፉልባክ ቦታ ያሉት አማራጭ ተጨዋቾች ሊቨርፑል ተለዋዋጭ ብቃት እንዲኖረው ያስችሉታል፡፡ ጆንሰን የክለቡ ተቀዳሚ የቀኝ መስመር ተከላካይ ነው፡፡ በሁለቱም እግሮቹ የመጫወት ችሎታው ባስፈለገ ጊዜ የሆዜ ኤንሪኬ ተለዋጭ እንዲሆን ተጨማሪ ዕድል ይሰጠዋል፡፡ ሆኖም የቀኝ መስመሩን ይዞ መቀጠሉ የማይቀር ይመስላል፡፡ በስተግራ የሚዋዥቅ ብቃት ቢኖረው እንኳን ሆዜ ኤንሪኬ ባለፈው የውድድር ዘመን በቂ አገልግሎት በመስጠቱ ቦታውን ጠብቆ ይቀጥላል የሚለው ግምት ሰፊ ነው፡፡
ከክለቡ አካዳሚ ያደገው አንድሬ ዊዝደም በመነሻው የመሀል ተከላካይ ነው፡፡ ይሁን እንጂ እንደ ብዙሃኑ ወጣት ተከላካዮች ሁሉ በ2013 የግሌን ጆንሰን ተቀያሪ ተደርጎ በሁሉም ውድድሮች በ19 ጨዋታዎች በቋሚነት ተሰልፏል፡፡ በአየር ላይ ጠንካራ ነው፡፡ ፍጥነቱም የሚደነቅ ነው፡፡ ማርቲን ኬሊም የመሀል ተከላካይ ሲሆን አብዛናውን የሊቨርፑል ተጨዋችነት ሕይወቱን በቀኝ መስመር ተከላካይነት አሳልፏል፡፡ በፉልባክነት በተጫወተባቸው በእነዚህ ጊዜት የጠቀማቸው አብይ ጉዳይ ከኳስ ጋር ያላቸው ችሎታ ነው፡፡ በማጥቃቱ ረገድ የግሌን ጆንሰን ያህል ላይሆኑ ይችላሉ፡፡ አሰልጣን ሮጀርስ እንደሚፈልጉት ኳስን በመጫወት የማይታሙ ተከላካዮች መሆናቸው ግን ተመራጭ ያደርጋቸዋል፡፡
በቀኝ ፉልባክነት እንዲጫወቱ በተጠሩ ቁጥር የሮጀርስን አንጀት የሚያርሱበት ሌላ ብቃትም አላቸው፡፡ የቡድኑ ተከላካይ ወደ መሀል ሜዳ ተጠግቶ ሲጫወት መስመሩን በመጠበቅ አይታሙም፡፡ ዊዝደምና ኬሊ የሊቨርፑል የነገዎቹ ተከላካዮች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ይሁን እንጂ ብቃታቸውን የበለጠ እንዲያጎለብቱ የበለጠ የጨዋታ ዕድል ማግኘት አለባቸው፡፡ በመጪው የውድድር ዘመን ሊቨርፑል ዩሮፓ ሊግ ላይ አይሳተፍም፡፡ ስሊሊህ ሮጀርስ ወጣቶቹን በካፒታል ዋን ዋንጫ እና በኤፍ.ኤ.ካፕ ላይ ሊያጫውቷቸው ይችላሉ፡፡ ከመደበኛው የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ይልቅ ተቀያሪዎችን ለማጫወት የሚመጥኑ ሌሎች ውድድሮች የሉምና፡፡
የቡድን ለውጥ
ሰባስቲያን ኮአቴስ በ2011 ኮፓ አሜሪካ ላይ ያሳየውን ብቃት በሊቨርፑል መድገም አልቻልም፡፡ በ2011/12 የአገር ስከርትል ጥምረት ውጤታማነት የቦአቴስን የጨዋታ ዕድል ገድቦበት ነበር፡፡ የመጫወት ዕድል ሲያገኝ ደግሞ ይርበተበታል፡፡ አይረጋጋም፡፡ 1.96 ሜትር የሚረዝመው ቁመቱ በአየር ላይ ጥቅም ቢሰጠውም በኦልድሃሙ ማት ስሚዝ ሲፈነጭበት ያሳየው ድክመት ደጋፊዎችን የሚያስጨንቅ ነው፡፡ ኮአቴስ ኳስን ሲይዝ መጥፎ ተጨዋች አይደለም፡፡ ነገር ግን ፍጥነት ይጎድለዋል፡፡ ኬሊ ወይም ዊዝደም አብረውት ከተሰለፉ ፍጥነቱን ከእነርሱ ጋር ለማስተካከል ይቸገራል፡፡ ቦታውን ጠብቆ የመጫወት ችሎታው ጥንካሬው ነው፡፡ በስፔን ወይም በጣልያን ክለቦች በውሰት ሲሰጥ በጠንካራ ጎኑ የበለጠ ማገልገል በቻለ ነበር፡፡ መጪው ዓመት የዓለም ዋንጫ የሚደረግበት እንደመሆኑ የዑራጓዩ ኢንተርናሽናል የቋሚ ተሰላፊነት ዕድል ካገኘ ለመመረጥ ይጠቅመዋል፡፡
ሊቨርፑል ማርቲን ስከርትልን በውሰት ለመስጠት ሀሳብ እንዳለው ተወርቷል፡፡ በፕሪሚየር ሊጉ ላይ አራት የውድድር ዘመናት ያሳለፈው ስሎቫኪያዊ ግን በውሰቱ ይጠቀማል ተብሎ አይገመትም፡፡ በእነዚህ ጊዜያት ከቋሚ ተሰላፊነት ይልቅ በተጠባባቂነትና ከዚያም በታች የሆነባቸው አጋጣሚዎች ይበዛሉ፡፡ ቢሆንም በጥሩ ያሳለፋቸው የውድድር ዘመናትም አሉ፡፡ በዕድሜው ለጋ ወጣት ባለመሆኑ ሊቨርፑልን የሚለቅ ከሆነ በቋሚ ዝውውር እንጂ በውሰት አይሆንም፡፡ በራስ መተማመኑን መልሶ ካገኘ ደግሞ ሊቨርፑል የስከርትል- አገርን ጠንካራ ጥምረት በድጋሚ ሊያገነው ይችላል፡፡ ሁለት የመሀል ተከላካዮች (ስከርትል እና ኮአቴስ) ሊቨርፑልን ሊለቁ የሚችሉበት ዕድል ካለ በያዝነው ክረምት ሮጀርስ የመሀል ተከላካይ የማስፈረም ከባድ የቤት ስራ መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ሊቨርፑል ረጅሙን የግሪክ ተከላካይ ኪሪያኮስ ፓፓዶፓሎስ ለማስፈረም ሙከራ አድርገዋል፡፡ከረጅም ጊዜ የጉልበት ጉዳት በኋላ በቅርቡ ጤንነቱን ማግኘቱ ተነግሯል፡፡ ከኳስ ጋር ባለተሰጥኦ ተከላካይ ሲሆን ተጋጣሚዎችን ይዞ ለማስቀረት የሚያስችል አካላዊ ጥንካሬ ባለቤትም ነው፡፡ ወደ አንፊልድ መምጣቱ እውን ከሆነ በቶሎ ወደ ቋሚ ተሰላፊነት የመግባት ዕድሉ ጠባብ ነው፡፡ ገና የ21 ዓመት ወጣት ሲሆን የእርሱ መኖር የማርቲን ኬሊን እና አንድሬ ዊዝደምን ዕድገት ያቀጭጫል፡፡ ዊዝደም በውሰት ካልተሰጠ በስተቀር፡፡
ሊቨርፑል በቦታው ሊገዛው ይችላል ተብሎ የሚጠበቀው ሌላው ተከላካይ ቲያጎ ሱሪስ ይባላል፡፡ ፍጥነቱና ከኳስ ጋር ያለው ችሎታ ጥሩ ይመስላል፡፡ አሰልጣኝ ሮጀርስ የሊቨርፑል ተከላካይ ግራ ክፍል የማጠናከር ፍላጎት እንዳላቸው በይፋ ተናግረው ነበር፡፡ ጃክ ሮቢንሰን መጪውን የውድድር ዘመን በብላክፑል እንዲያሳልፍ በውሰት ተሰጥቷል፡፡ ከአርሰናል ጋር ሲጫወቱ ቲዮ ዋልኮትን በመጋፈጥ ተስፋ ሰጪ ብቃት አሳይቶ ነበር፡፡ ሆኖም ብላክፑል ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ለመመለስ በሚያደርገው ትግል ላይ ለአንድ የውድድር ዘመን ከተሳተፈ የተሻለ ተጨዋች ይሆናል የሚል ግምት አለ፡፡ የቤንፊካው ሎሬንዞ ሜልጋሬዮ የጆዜ ኤንሪኬ ተጠባባቂ ይሆን ዘንድ ወደ ሊቨርፑል ሊመጣ ይችላል፡፡ የቫሌንሲያው ዓሊ ሲሶኮም በቀዮቹ ለዝውውሩ ከታጩት የግራ መስመር ተከላካዮች አንዱ ነው፡፡ የ25 ዓመቱ ፈረንሳዊ ባለው የቦታ አያያዝና አጠባበቅ ብቃትና የመከላከል ጥንካሬ የተሻለ ተመራጭ ይመስላል፡፡
በግዢ ከማምጣት ይልቅ ወጣቶችን ማሳደግ ካስፈለገ የሊቨርፑል አካዳሚ አሰልጣኝ ከዋናው ቡድን ጋር አልፎ አልፎ የሚጫወት ተከላካይን እንዲጠቀሙ ሊደረግ ይችላል፡፡ የ17 ዓመት ሰሜን ዌልሳዊ ሎይድ ጆንሰን ሰሜን አየርላንዳዊው የቀኝ መስመር ተከላካይ ሪያን ማክላፍሰን ከአካዳሚው ሰልጣኞች አይን ውስጥ ይገባሉ፡፡ ማክላፍሰን ከአንድ ዓመት በፊት በዝግጅት ጨዋታ ላይ በአሜሪካ ከፍሪንቼስካ ቶቲ ጋር ተጋፍጦ ነበር፡፡ በመጪው የውድድር ዘመን በፕሪሚየር ሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን መጫወቱ የማይቀር ነው፡፡ የ19 ዓመቱ ብራድ ስሚዝ ባሳለፍነው የውድድር ዘመን መጨረሻ ላይ በሊቨርፑል ዋናው ቡድን ውስጥ ለተጠባባቂነት የበቃ ቢሆንም ጉዳት ህልሙን እውን እንዲያደርግ አግዶታል፡፡
ሊቨርፑል ረጅም ጊዜ ያገለገለውን ካራገርን ቢያጣም የአካዳሚው ተስፋዎችን ጨምሮ አማራጭ ተስፋዎች አሉትት፡ አሰልጣኝ ሮጀርስ የሚወስዱት እርምጃ ሁሉ ተከላካይ መስመሩን ለረጅም ጊዜ ከመገንባት አንፃር እንደሚሆን እርግጥ ነው፡፡ ሩቁን ማሰብ ብቻ አላማ አይሆንም፡፡ በቅርቡም ሊቨርፑልን ወደ ቻምፒየንስ ሊግ መመለስ የሚችል ተከላካይ መስመርም እንደሚያስፈልጋቸው ይረዳሉ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ያላቻ ጋብቻ (ከይድነቃቸው ከበደ)

0
0

semayawi party
የሰማያዊ ፓርቲ ያላቻ ጋብቻ
መንግስት ተግባሩን ሣይወጣ ቀርቶ መንደርተኛና ቧልተኛ ሲሆን እንዴት ያሳፍራል ! ይህን ለመፃፍ ያነሣሣኝ አዲስ ዘመን ጋዜጣ “ የሰማያዊ ፓርቲ ጥቁር ተግባራት ” በሚል በገፅ 3 አጀንዳ ላይ እንዲሁም በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪን በተጨማሪ ዛሚ ሬዲዮ ጣቢያ የክብ ጠረጴዛ ውይይት እና በሬዲዮ ፋና በዜና እና በልዩ ዘገባ የሚተላለፉ ፕሮግራሞች፤በተለያዩ አካባቢዎች በሚካሄዱ ጥቃቅን አነስተኛ ስብሰባዎችና ሰልፎች የሚሰሙ መፈክሮች የመንግስትን ፍርሃቱን እና ውንጀላ በሚገባ የሚያሳዩ በመሆናቸው ነው፡፡
መንግስት ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ለጥያቄ አቅራቢዎች የሚያስርበት እና የሚያሰቃይበት አዋጅ ማውጣት ይቀለዋል፤ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም መነሻውን 4 ኪሎ የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት መድረሻውን ኢትዮ-ኩባ አደባባይ ያደረገ ታላቅ የተቃውሞ ሠልፍ ተደርጓል፡፡ በዕለቱም ለመንግስት የቀረበለት ጥያቄ የሰብዓዊ ጥሰቶች እንዲስተካከሉ፣የታሰሩ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ፣በዓይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባት እንዲቆም በዚህም ምክንያት የታሰሩት እንዲፈቱ፣የኑሮ ውድነቱ ማሻሻያ እንዲደረግበት እና የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ የሚል ጥያቄዎች ናቸው፤እጅግ በሰለጠነ እና ሠላማዊ በሆነ መንገድ ጥያቄው ለመንግስት የቀረበ ሲሆን መንግስትም ለዚህ ምላሽ የሦስት ወር የጊዜ ገደብ ተሰጥቶታል፡፡
ይሁን እንጂ መንግስት ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ስም ማጥፋት ዘመቻውን ቀጥሎበታል፤መንግስት ስም ለማጥፋት ብሎ ያነሳቸው አንኳር ሀሳቦች መሰረታዊ የሰው ልጅ ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ናቸው፡፡ መንግስት ይህን ለመረዳት ተጨማሪ 22 ዓመታት ቢያስፈልገውም ህዝብ ግን ያጣውን ነፃነት ለማግኘት ትግሉን ይቀጥላል፤ ለህዝብ የመብት ጥያቄ የሆኑት መንግስት ለመወንጀል የሚያነሳቸው ሃሳቦች በጥቂቱ እንመልከት፡፡
1ኛ. “በ1997 ዓ.ም በቅንጅት ተሳትፎ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው ዛሬ ደግሞ በአዲስ ኮፍያ የሚንቀሳቀሱ” የተባለው ቁጥር አንድ ውንጀላ ነው፤ ምላሹ ደግሞ ፡- ይህ ሀሳብ ከእውነት የራቀ አይደለም ከዛሬ 8 ዓመት በፊት በሺዎች የሚቆጠሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ይቅሩና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ለነፃነት እና ለመብት ከፍተኛ አስተዋፅኦ የተደረገበት ወቅት ነው፤ በወቅቱ ለሚፈለገው ነፃነት ደም ተከፍሎበታል፡፡ አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ባዶ እጁን አደባባይ ወጥቶ “ድምፃችን ይከበር” በማለቱ አገርን ሊወር እንደመጣ ጠላት በመከላከያ ሠራዊት ለዛውም በሰለጠኑ ነፍሰ ገዳይ ታሪክ ሁሌም የሚዘክራቸው ኢትዮጵያውያን በግፍ ገሏል፤ በዚህም ምክንያትና በሌሎች የሚፈለገው ነፃነት ታጥቷል፡፡ እናም ያኔ ያጣነውን ነፃነትና መብት መንግስት በአዲስ ኮፍያ ቢለውም እጅግ በሠለጠነና ሠላማዊ በሆነ መንገድ በአዲስ እስትራቴጂ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በፈቀደው መልክ ተደራጅቶ ይህን አምባገነን ስርዓት ታግሎ ለማሸነፍ የሚያደርገው ጥረት ወንጀል የሚሆነው ምኑ ላይ ነው?
2ኛ. “በውጭ ከሚገኙ ፅንፈኛ አክራሪ ኃይል ጋር በመቀናጀት በአረቡ ዓለም የታየውን አብዮት ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት” ይህ ሁለተኛው ውንጀላ ነው፤ ሌባ አባት ልጁን አያምንም የሚባለው ተረት ለዚህ ውንጀላ ተስማሚ ይመስለኛል ምክንያቱም ያሁን መንግስት የበፊት አማፅያን (ወያኔዎች) ከሱዳን፣ ከሶሪያና ከግብጽ ከመሳሰሉት አገራት የጦር መሣሪያና ስልጠና እንዲሁም መሸሸጊያ በማግኘት አዲስ አበባ ቤተ መንግስት መግባታቸውን የሚታወቅ ነው፤ እነሱ በክደት የፈጸሙት ሁሉ ሌላው ያደርገዋል የሚል ከንቱ አሳብ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ የተመሠረተው በኢትዮጵያውያን ነው ትግሉም ሆነ ዉጤቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው፤ ሌላው ደግሞ በአረቡ አለም የታየው አብዮት ኢትዮጵያውያን ከ8 ዓመት በፊት በአስደናቂ ሁኔታ የተገበርነው ነው፡፡ ዛሬ ደግሞ ከ8 ዓመት በፊት ያጣነው አብዮት መንግስት አልሰማና አልለወጥ ካለ የአረቡን አብዮት በኛ አገር ተጨባጭ ሁኔታና ማህበራዊ ንቃተ ህሊና ሠላማዊ በሆነ መንገድ በመስቀል አደባባይ ወጥተን ብናደርገው ወንጀሉ ምኑ ላይ ነው?
3ኛ. “ከውጭ አሸባሪ ግንቦት ሰባት ቴሌቪዥን ጣቢያ ‘ኢሳት’ ጋር በመቀናጀት” ይሄ ደግሞ ሦስተኛ ውንጀላ ነው በመሠረቱ በአገር ቤት ያለው የዳኝነቱ ስርዓት እውነተኛ ፍትህ የሚሠጥ ቢሆን ኖሮ “መልካም ስምና ዝናን በማጉደፍ በተጨማሪም መረጃን የማግኘት መብት በመንፈግ” የወንጀል ክስ መመስረት ይቻል ነበር ግን ምን ዋጋ አለው?፡፡ ይህን ለማለት የፈለኩት አንደኛ ኢሳት መረጃን ለተጠሙ በዓለም ላይ የሚገኙ ኢትዮጲያውያን አይንና አንደበት የሆነ ሚዲያ እንጂ የግለሰብ ወይም በተወሰኑ ቡድኖች የሚንቀሳቀስ ሚዲያ አይደለም፡፡ እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ሚዲያው የእገሌ ድርጅት ነው መባሉ የስም ማጥፋት ወንጀል ነው፡፡ በሁለተኛ ደረጃ መረጃን ማግኘት ህገ መንግስታዊ መብት ነው፤ ይሁን እንጂ በአገራችን እኛ የመረጥነው ሳይሆን መንግስት የመረጠልን ሚዲያ ነው የምንመለከተው፣ የምንሰማውና የምናነበው ለዚህም ማሳያ በአገር ውስጥ ትክክለኛ መረጃ የሚያስተላልፉ ጋዜጠኞች መጨረሻቸው ስደት ወይም እስራት ነው፤ ከሀገር ውጭ ያሉ ሚዲያዎች ደግሞ ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ ይታፈናሉ በዚህ ምክንያት መረጃ የማግኘት መብታችን በኃይል ተከልክለናል፡፡
4ኛ. “የጥቂት ሙስሊም አክራሪዎች አጀንዳ በመደገፍ አደባባይ ይዞ መውጣት” አራተኛ ውንጀላ መሆኑ ነው፤ ጥቂት፣ አነስተኛ፣ ጥቃቅን የመንግስት አፍ መፍቻ ከሆኑ ሰነባብተዋል፤
“ጥቂቶች ቆራጦች ያልተንበረከክነው
ዛሬን እንሞታለን ነገ ታሪክ ምስክር ነው”
የሚለው የእናንተ የትግል መዝሙር አስታወሰኝ እባካችሁ ትላንትና ለጥቂቶች የነበራችሁ ከፍተኛ ግምት ዛሬ የት ገደል ገባ? የሙስሊም ወንድሞቻችን ትግል የጥቂቶች አይደለም የአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ሙስሊም የሀይማኖት ነፃነት ጥያቄ ነው፡፡ በመሆኑም ለአገር የቆመ ፓርቲ ለመብትና ለነፃነት በሰላማዊ መንገድ እታገላለሁ እያለ መብትና ነፃነታቸውን ለማስመለስ ደከመን ሰለቸን ሳይሉ “ድምፃችን ይሰማ” ለሚሉ እውነት ነው ድምፃቸው ይሰማ ብሎ ሰማያዊ ፓርቲ ድምፁን ቢያሰማ የሚያስወነጅለው ምክንያቱ ምንድን ነው?
5ኛ. “ሰማያዊ ፓርቲ ሠልፍ ላይ መካከለኛ እድሜ ላይ ያሉና አዛውንቶች ጭራሹንም በሰልፉ ላይ የሉም በአብዛኛው ለአክራሪዎች ወግኖ የቆመ ኃይል ነው” ይሄ በአምስተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ከውንጀላ ይልቅ በኢህአዴግ ቋንቋ የሠልፉን ገፅታ ጥላሸት ለመቀባት ነው፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ታላቅ የተቃውሞ ሠልፍ ሁሉንም የህብረተሠብ ክፍል ያካተተ እንደነበር የአለም ሚዲያ የዘገበው ነው፤በጣም የሚገርመው በ1997 ዓ.ም አደባባይ የወጣውን ወጣት “ አደገኛ ቦዘኔ ” በማለት ሠልፈኛውን እና የሠልፉን ዓላማ የተለየ ለማድረግ መንግስት ያልፈነቀለው ድንጋይ የለም፡፡ አሁን ደግሞ ከ8 ዓ.ም በኋላ በተካሔደው የተቃውሞ ሰልፍ ወጣቱ ብቻ ነው የተገኘው በማለት ለወጣቱ ያለውን ንቀት መንግስት በድጋሚ አረጋግጧል፡፡ እኔ የምለው! ወጣቱ ስለሀገሩ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳይ አያገባውም እንዴ? በተጨማሪም ተገፋን፣ ተበደልን ከሚሉ ሰዎች ጋር ወግኖ መቆም ጥፋቱ ምን ላይ ነው? በኢትዮጵያ ውስጥ በመንግስት ታስቦና ታቅዶ የሚፈፀም በደልና መገፋት በኔ አልደረሰም ተብሎ እንዴት ይታለፋል፤ ዛሬ ከተገፉትና ከተበደሉ ወገኖች ጋር ወግኖ ያልቆመ ነገ ለሱ ማን ሊቆምለት ነው?
በአጠቃላይ ከላይ የተገለፁት ሀሳቦች በመንግስትና ካድሬዎች እና ሚዲያዎች የሚነዙ አሉባልታ ወሬዎች መሆናቸውን ለማሳያት ለመንደርደሪያነት የቀረበ ፅሁፍ ነው፡፡ መንግስት ከሰሞኑ የተያያዘው ነገር ቢኖር ከስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍ ባለ ሁኔታ የሃይል እርምጃ መውሰድ ነው፤ለዚህም ማሳያ በተለያዩ ከተሞች በእስልምና እምነት ተከተዮች ላይ ግድያ እና ድብደባ እንደሁም እስራት እየተካሄደ ነው፤ ቀጣዩ ደግሞ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትና አመራሮች መሆናቸው የዘፈን ደርዳርታ እስክስታ ነው እንደሚባለው ከጠቅላይ ሚኒስተሩ ጀምሮ እስከታችኛው የስልጣን እርከን የተቃዋሚ ፓርቲ በተለይ ሰማያዊ ፓርቲን መንግስት የነገር አባት ( ሽማግሌ) በመሆን በቅርብ ከማያገኛቸው ነገር ግን እንዲህ አይነቱን ውንጀላ ለመፈረጅ ከሚመቻቸው ከግንቦት ሰባት እና ከሙስሊም አክራሪዎች ጋር ፓርቲውን እየዳሩት ይገኛል ፤ጋባቻው ግን ያላቻ ጋባቻ ነው፡፡
በመሆኑም መንግስት በተሠጠው ጊዜ አላፊነቱን በመወጣት እኛ ተበዳዮቹ ብቻ ሳንሆን እናተም በዳዮቹን በጋር በነፃነትና በእኩልነት የምንኖርበት አገር በማቅናት ሁሉ በህግ ፊት እኩል ሆኖ የሚዳኝበትን ጊዜ እናቅርበው፤ አለበለዚያ የምትፈሩት ህዝባዊ አብዮት መምጫው ቀን እሩቅ አይደለም፡፡
ይድነቃቸው ከበደ
የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ሃላፊ

 

የፍቼዉን የአንድነት ሰልፍ የሚያስተባብሩ ሁለት ኢትዮጵያዉያን ተደበደቡ

0
0

UDJ_ETHIOPIA-231x3001

 

የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል መርህ የአንድነት ፓርቲ የሚያደርጋቸዉን፣  አገረ ሰፊ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎቹን በስፋት ገፍቶበታል። በኦሮሚያ በሚገኙ ሶስት ታላላቅ ከተሞች፣ አዳማ/ናዝሬት፣ ባሌ ሮቢና ፍቼ ሰላማዊ ሰልፎች እንደሚያደርግ፣  ለከተሞቹ ባለስልጣናት ያሳወቀ ሲሆን ፣ ቅስቀሳዎችንም በስፋት አያደረገ ነዉ።

 

ከጥቂት ሰዓታት በፊት ፣ ሰላማዊ ሰልፉን ለማስተባበር ወደ ፍቼ ያቀኑ ሁለት የአንድነት ፓርቲ አሰተባባሪዎች በአገዛዙ ካድሬዎች ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው ሲሆን፣ ከወዲሁ በሕገ መንግስቱ የተቀመጠዉን የዜጎች መብት ለመርገጥ ኢሕአዴግ እየሰራ መሆኑን በግልጽ የሚያሳይ ነዉ። የፓርቲዉ አመራር አባላት በዚህ ጉዳይ ላይ በስፋት መግለጫ እንደሚሰጡም ለማወቅ ችለናል።

የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በደሴ፣ በጎንደር፣ በባህር ዳር፣ በአርባ ምንጭ፣ በጂንካ ሰላማዊ ሰልፎች በወላይታ ሶላማዊ ሰልፎችን፣ በአዲስ አበባና በወላይታ ሶዶ ደግሞ  የተሳኩ ሕዝባዊ ስብሰባዎች ማድረጉ ይታወቃል።

ዋ! እዮብ መኮንን! –‹‹እግዚአብሔርን ባገኘው የምጠይቀው የዘላለም ሕይወት እንዲሰጠኝ ነው››

0
0

eypbበአቤል ዓለማየሁ

ጊዜው ከአምስት ዓመት በፊት ነው፤ በሚሊኒየሙ፣ ሚያዚያ ወር የመጀመሪያ ሳምንት፡፡ ሠራበት በነበረው ጐግል ጋዜጣ ‹‹ጥበብ›› አምድ ላይ እንግዳ ላደርገው ረፋድ ላይ ወደ እዮብ መኮንን የእጅ ስልክ መታሁ፡፡ መልካም ፈቃዱን ገለጾ… አንጃ ግራንጃ ሳያበዛ ‹‹ከተመቸህ ዛሬ መገናኘት እንችላለን›› አለኝ፡፡ ትንሽ መዘጋጀት እንዳለብኝ ነግሬው ዛሬ ከሆነ ምሽት ላይ መገናኘት እንደምንችል ነገርኩት፡፡ ጥያቄዎች ሳሰባስብ እና ሳሰላስል ዋልኩ፡፡ የቀጠሮ ቦታ ስላልቆረጥን ከመገናኘታችን በፊት ልደውልለት ተስማማን፡፡ ደወልኩለት!

‹‹ፒያሳ አካባቢ ነኝ፡፡ እዚህ መምጣት ትችላለህ?›› (እዮብ)
‹‹መልካም ግን ትንሽ እንዳልቆይብህ መገናኛ አካባቢ ነኝ፡፡ መሀል ላይ መገናኘት ከቻልን መልካም ነው፡፡ አለበለዚያ ግን ልምጣ››
‹‹እሺ! የት እንገናኝ? መኪና ይዘሀል?››
‹‹መኪና? ይሄ አራት ጎማ ያለው ነገር?››
‹‹ይስቃል››
‹‹አለኝ ግን butter fly ነው፡፡ (የልብስ ስፌት መሆኑን ልብ ይሏል፡፡) ከቤት ውጪ አልነዳውም››
እየሳቀ ‹‹እሺ! የት ልምጣልህ››
‹‹ዑራዔል አካባቢ አማካይ ስፍራ ነው፡፡ ፕላዛ ሆቴል እንገናኝ?›› እውነት ለመናገር እኔ የነበርኩት ፕላዛ አካባቢ ይገኝ የነበረው ቢሯችን ውስጥ ነበር፡፡ የጀመርኩትን ሥራ ሳጠናቅቅ፣ ኮምፒውተር ስዘጋጋ፣ እንዳልቆይበት ብዬ ግርጌዬ ላይ እንዲመጣ ጨከንኩበት፡፡ የሚገርመው እኔ ቢሮ ስድበሰበስ እሱ ቀድሞ ፕላዛ ደረሰ፡፡ ሮጥ ብዬ ስደርስ ሆቴሉ ግቢ ውስጥ ጥቁር ቪታራ መኪናውን እየዘጋጋ ነበር፡፡ ሆቴሉ ምግብ አዳራሽ ውስጥ ገበታ ሳይቆርሱ መስተናገድ ባይፈቀድም ቃለ ምልልስ ለመስራት ሳስፈቅድ ይሁንታ አገኘሁ፡፡ የሆቴሉ ባልደረቦች ድሬድ ጸጉሩን የተሸለተውን እዮብን እያዩ ‹‹እሱ ነው/አይደለም›› እየተባባሉ ነበር፡፡
አማርኛ፣ ትግሪኛ፣ ኦሮምኛና ሱማሊኛ ቋንቋዎችን አቀላጥፎ እንደሚናገር የነገረኝ እዮብ ቃለ ምልልሱን ከመጀመሬ በፊት ማስጠንቀቂያ አስቀመጠ፡፡
‹‹በድምጽ መቀዳት ስለማልፈልግ፣ ወረቀት እና እስክሪብቶ አውጣ››
‹‹ለምን››
‹‹ከዚህ በፊት ያላልኩትን ብለው መጽሔት ላይ ስላወጡ ይሄን ስህተት መድገም አልፈልግም፡፡ ስለዚህ እየጠየቅከኝ መልሱን ጻፍ!››
‹‹እኔ እንዲህ እንደማላደርግ ከመቶ ፐርሰንት በላይ ቃል ልገባልህ እችላለሁ››
‹‹ኖ! አይሆንም››
ላሳምነው ሞከርኩ፡፡ ሊዋጥለት አልቻለም፡፡ በዚያው ሰሞን አንድ መጽሔት ያልዘፈነውን ራጋ ‹‹የራጋ ስልት ያለው እንትን የተሰኘ ዘፈኑ›› እያለ አልበሙን ጥንብ ርኩሱን አውጥት ስለነበር ፕሬሱ ላይ ያለው እምነት የበለጠ እንዲሸረሸር አድርጎታል፡፡ የመጨረሻ አማራጭ ልሰጠው ጉሮሮዬን ጠረግኩ፡፡
‹‹እውነት ለመናገር መልስህን በቃል እየጻፍኩ አልዘልቀውም፡፡ በዚህ ላይ እኔ እስክፅፍ ስትጠብቅ ሃሳብህ ይቆራረጣል፡፡ ለዛ ቢስ ቃለ ምልልስ ይሆናል፡፡ ማድረግ ያለብኝ [ተገቢ ነው ብዬ ባላምንም] እስከዛሬም ለማንም አድርገነውም ባናውቅም ድምጽህን ወደ ወረቀት ከገለበጥኩ በኋላ (After transcription) አምጥቼ ላሳይህ እችላለሁ፡፡ አለበለዚያ ግን በቃል…››
አመነታ፡፡ እንደምንም አሳመንኩትና ‹‹ሽጉጤን›› ተረክ አደረግኳት [ለእንደ እኔ አይነት ጋዜጠኛ ተብዬ ሽጉጡ ድምጽ ማስቀሪያው ነች፡፡] አወራን፡፡ በቀጣዩ ቀን ምሽት ላይ ይሰራበት የነበረው ፋራናይት ክለብ (ልምምድ ላይ የነበረ ይመስለኛል) ወስጄ አሳየሁት፡፡ አነበበውና ምንም ሳያንገራግር በደስታ ሸኘኝ፡፡ ከዚያም የሚያዚያ 10/2000 ዓ.ም ጐግል ጋዜጣ ላይ ጨዋታውን ዳርኩት፡፡ ካወራናቸው ውስጥ ጥቂቱን እንካችሁ፡፡

የተለያዩ አይነት የሬጌ ስልቶች አሉ፡፡ አንተ የምትጫወተው የትኛውን አይነት ነው ትክክለኛ (Pure የሆነውን) ሬጌ ትጫወተዋለህ
ሬጌ የተለያየ አይነት ስታይል አለው፡፡ ሩትስ፣ ስካ፣ ዋን ድሮፕና ሌሎችም አሉ፡፡ የምቱ ሁኔታ ነው ሩት፣ ስካ… ሊያስብለው የሚችለው፡፡ እኔ ሁሉንም የሬጌ ቶን እጫወታለሁ፡፡ ስለ እኔ መናገር ቢከብደኝም ሙዚቃ የሚያውቁ ሰዎች በአብዛኛው በትክክል እንደምጫወተው ይናገራሉ፡፡

‹‹ይዞ የመጣው ለአገራችን አዲስ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊያሰልፈው የሚችል አዘፋፈን ነው፡፡ ሬጌ የሚፈልገው ነገር አለው፡፡›› ተብሎ ስለ አንተ የተጻፈ ጽሁፍ አንብቤያለሁ፡፡ በዚህ ትስማማለህ?
ጸሐፊው ያመነበትን ጽፏል፡፡ እኔ ከምናገር አድማጭ ቢፈርድ ጥሩ ነው፡፡

በሙዚቃ ስራህ ላይ ተጽዕኖ ያሳደረብህ ሰው አለ?
አሊ ቢራ እና ቦብ ማርሌይ በጣም የምወዳቸው ድምጻዊያን ናቸው፡፡ የእነሱ ተፅዕኖ አለብኝ፡፡ የሁለቱንም ዘፋኞች ዘፈን ከልጅነቴ ጀምሮ እሰማም፣ እዘፍንም ነበር፡፡

ሬጌ ሙዚቃ መጫወት ያለበት ሰው ምን ማሟላት አለበት?
መጀመሪያ ሙዚቃውን ማፍቀር አለበት፡፡ ከዚያም በደንብ መስማትና ደጋግሞ ልምምድ መሥራት ይኖርበታል፡፡

በአልበምህ ላይ የሰራሀቸው ዜማዎች ተመሳሳይነት አላቸው ይባላል፡፡
በፍጹም አይመሳሰሉም፡፡ ለአንድ የውጪ አገር ዜጋ የትግሪኛ ዜማ ብታሰማው ሁሉም አንድ ዓይነት ነው የሚመስለው፡፡ የእኔም እንደዚያው ነው፡፡ አሰማማችን ነው እንጂ ዜማዎቹ አይመሳሰሉም፡፡

አልበምህ ያሰብከውን ያህል ተደምጧል?

ገና ነው ብዬ ነው የማስበው፡፡ ሰውም በበቂ ሁኔታ የሰማው አይመስለኝም፡፡ የተወሰነ ሰው ግን ሰምቶታል፡፡

ለምሳሌ የሚካያ በኃይሉ አልበም ከወጣ ጀምሮ (1999 ዓ.ም.) የወደዱት ቢሆንም ይበልጥ የተሰማው እየቆየ ሲሄድ ነው፡፡ ያንተም አልበም እንደዚያ…
እመኛለሁ ግን እንደዚያ ይሆናል ብዬ አላስብም፡፡ አምላክ ነው የሚያውቀው፡፡

‹‹እዮብ በአብዛኛው የሚጫወተው የሬጌ ዘፈኖችን ስለሆነ ጸጉሩ መለያው ነበር፡፡ ሲቆረጠው ዘውዱን የተገፈፈ ንጉስ መስሏል ያሉኝ አሉ፡፡

ለእነሱ የሚታያቸው እንዳልከው ሊሆን ይችላል፡፡ እኔ ግን በመቆረጤ ደስተኛ ነኝ፡፡

መቼና ከማን ጋር ስትሆን ደስ ይልሀል?

ለብቻዬ፣ ከጓደኞቼ ጋር ስሆንና መጽሐፍ ቅዱስ ሳነብ ደስ ይለኛል፡፡ ሁሌም አዲስ ስለሆነ ባነበብኩት ቁጥር ይገርመኛል፡፡ ያነበብከውን መተግበር ስትጀምር ይበልጥ አዲስ ይሆንብሀል፡፡ ሌላ መጽሐፍ ማንበብ ትቼያለሁ፡፡

eyob mekonen 2ትልቁ ራዕይህ ምንድን ነው?
አላውቀውም፡፡ ዛሬን ብቻ መኖሬን ነው የማውቀው፡፡ በፕሮግራም ነገ እንዲህ አደርጋለሁ አልልም፡፡ አስተማሪና መካሪ ዘፋኝ ብሆን ደስ ይለኛል፡፡ ስለ ነገ የሚያውቀው እግዚአብሔር ነው፡፡

አሁን የምትኖረው ሕይወት እና ያለህበት ደረጃ የምትፈልገውን ዓይነት ነው?

ኑሮዬ ይበቃኛል ማለት ትልቅ ነገር ነው፡፡ ደስተኛ ነኝ፡፡ ሕይወት ደግሞ የምትጣፍጠው አማራጭ ስታጣ ነው፡፡ በሕይወቴ ከዚህ በላይ ብሆንም ካለሁበትም ዝቅ ብልም ምንም አይመስለኝም፡፡ አማራጩ እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡

በቆይታችንየእግዚአብሄርንስምደጋግመህአንስተሀል፡፡ብታገኘውበቀዳሚነትየምታነሳለትጥያቄምንድንነው?
የዘላለም ሕይወት እንዲሰጠኝ ነዋ!

በደረሰበት ደንገተኛ ህመም ቅዱስ ገብርዔል ሆስፒታል ሲታከም የነበረው ከዚያም ለተሻለ ሕክምና ወደ ናይሮቢ አቅንቶ ሳይነቃ በሳምንቱ መጨረሻ ሕይወቱ ያለፈው ተወዳጁ ድምጻዊ እዮብ መኮንን ጋ ያኔ በተገናኘንበት ወቅት አልበሙ እንዲህ ይገናል ብሎ አላሰበም፡፡ ‹‹ታያለህ እንደ ሚካያ አልበም ነው የሚሆነው›› ብዬ ‹‹ስጠነቁል›› አልመሰለውም ነበር፡፡ ሥራው ከገነነ በኋላ ‹‹አላልኩህም ነበር!›› ብዬ ከመፎከር አልቦዘንኩም፡፡ አንድ ቀን አጋጣሚ ቦሌ አካባቢ አግኝቼው አንድ ካፌ ትንሽ ተቀምጠን አወራን፡፡ አወራን ከማለት ይልቅ መጽሐፍ ቅዱስ ሲሰብከኝ ነበር ማለት ይቀላል፡፡ ልቡ ተሰብሮ፣ ግንኙነቱ ከአምላኩ ጋር ብቻ ይመስል ነበር፡፡ ዛሬ በ9 ሰዓት በሥላሴ በተፈጸመው የቀብር ስነ-ስርዓቱ ላይ ጥቅምት 12/1967 ዓ.ም. መወለዱ የተነገረው እዮብን ሁኔም በማይሰለቹ ዜማዎቹ እናስታውሰዋለን፡፡ በርካታ ሰውም በቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በመገኘት ሀዘኑን ገልጿል፡፡ እንደተመኘውም በላይኛው ቤት ‹‹የዘላለም ሕይወት እንዲሰጠው›› እመኛለሁ፡፡ ዋ! እዮብ! ከልቤ አዝኛለሁ! ነፍሱን ይማረው!

መለስና ደሃ ዘመዶቹ

0
0

ክፍሉ ግርማ

ሰሞኑን የቀድሞውን የዲክታትር መለስ ዜናዊ የሞተበትን አንደኛ ዓመት በማስመልከት በየድረገጹ የተለያዩ የተቃውሞም የድጋፍም ጽሁፎች እየወጡ ነው ከሁሉ ግን አውራምባ ታይምስ በተሰኘው ድረገጽ ላይ አንድ ስለ መለስ ወንድምና እህት የሚገልጽ ፊልም አየሁ ነገሩ ሁሉ በጣም ገረመኝ ብዙ አስተያየቶችንም አነበብኩ ለእኔ ግን የማይውጥ ነው!! በጣም ስለድሃ ይሚያስብ ታላቅ መሪ…. ዘመዶችን እንኳን ለሃገሩ ሲል የረሳ መሪ…..ወ.ዘ.ተ እነዚህን የመሳሰሉ ውደሳዎችን የሚወዱት ኮሚኒስቶች ብቻ ናቸው

አንድ ሃይማኖት ያለው ወይም በትክክል የሚያስብ ሰው እንዴት ዘመዶችን ይረሳል በክርስትናም ሆነ በሙስሊሙ እምነት እናትና አባትን ከዚያም ወንድምና እህትን ማክበር መረዳዳትም እንዳለብን ያስተምራል.. አሁን እስቲ ይታያችሁ የመለስ እህት ጠላ መሸጥ ማለት መለስ ታላቅ መሪ ማለት ነው ? እዚህ አሜሪካን ሃገር በቀን 16 ሰዓት ከባድ ስራ እየሰሩ ወይም በአረብ አገር እህቶቻችን 24 ሰዓት በሰው ሰራተኛነት እይተቃጠሉ ወንድምና እህቶቻቸውን የሚስተምሩ ከቻሉም በብዙ ሺ የሚቆጠር ብር እየከፈሉ ከሃገር ወጥተው ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርጉት ቤተሰባቸውን ለመቀየር አይደለምን? በሃገራችንም አንዱ ከቤተሰብ የተሻለ ቦታ ካለ ሌላውን መርዳትም የተለመደ ባህላችን ነው ወደ ቁም ነገሩ ለመለስና በእኔ እምነት መለስ እነዚህን ደሃ ወንድምና እህቱን አይውዳቸውም ወይም ያፍርባቸዋል ያልተማሩና ደሃ ስለሆኑም ይሆናል ወይም ሌላ ሚስጢር አለ እንጂ ለነዚህ ሚስኪን ሰዎች መለስ ትንሽ ቦታ አጥቶ አይደለም ለመሆኑ እነዚህ ወንድምና እህት ቤተመንግስት ለቅሶ ለመቀመጥ ተፈቅዶላቸው ይሆን በቀብር ስነ ስረአቱ ላይስ….ወ/ሮ አዜብስ ኤፈርት ካሰራቸው ብዙ ፋብሪካዎች በአንዱ ተቀጥረው ትንሽ ከጠላ ሻጪነት ብትገላግላቸው ጥሩ ነበር ኤፈርት የትግራይ ህዝብ ሀብት አይደለም እንዴ? ለመለስ እህት ያልሆነ ለማን ሊሆን ነው?

ከክፉ ውንድም ይጠብቅዎ

ፍልሙን ለማይት

አምስተኛው ባርነት –ከፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)

0
0

ቤቶችበጥንቱ ስርዓት፣ አንድ ሰው ከአራቱ በአንዱ መንገድ ባሪያ ይሆናል። የመጀመሪያው በጦርነት ተሸንፎ ከተማረከ ፣ ሌላው እዳውን መክፈል አልችል ብሎ በእዳ ከተያዘ ፣ ሶስተኛው ከባሪያ ቤተሰብ የተወለደ ከሆነ በውርስ፣ አራተኛው ደግሞ ባሪያ ፈንጋዮች ይዘው ከሸጡት ነው። በዚህ ዘመን የባሪያ ንግድ ቢጠፋም፣ ባርነት ግን አልጠፋም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እንዲያውም አምስተኛውን የባርነት መንገድ እያየን ነው፤ ይሄ ባርነት በባህሪው እስከዛሬ ከታዩት ሁሉ የተለየና አስገራሚም ነው። እመለስበታለሁ።
ባሪያ ማለት፣ የጌታውን እጅ አይቶ የሚያድር፣ በራሱ ነጻነት የሌለው፣ ሰምቶ የመቀበል እንጅ ሰምቶ የመመለስ መብት የሌለው፣ በግዑዝና በነጻ-ሰው መካከል ያለ ፍጥረት ነው። ባርያ ሰውን ሰው የሚያደርገውን ነጻነት ሙሉ በሙሉ የተገፈፈ በመሆኑ፣ ከሰው ተርታ የሚመደበው ስለሚመገብ፣ ስለሚለብስ፣ መጠለያ ስላለው፣ ቋንቋ ስለሚጠቀም እና አውራጣት ስላለው ብቻ ነው፤ ከዚያ በተረፈ ግን የጭነት እንስሳ ማለት ነው። ባሪያ በእግዚአብሄር አምሳል በመፈጠሩ ክፉና ደጉን የመለየት ስልጣን ቢሰጠውም ፣ ስልጣኑን በጌታው በመነጠቁ ፣ ሁልጊዜ የጌታውን ደግ ነገር ብቻ እያየ እና እያመሰገነ የሚኖር ፍጥረት ነው።

በአሁኑ ጊዜ የሚታየው አምስተኛው የባርነት መንገድ 40 በ60 ከሚባለው የቤት ግንባታ ጋር የተያያዘ ነው፤ በዚህ የባርነት መንገድ ለመጓዝ የወሰነው ደግሞ ዲያስፖራው ( በውጭ የሚኖረው) ኢትዮጵያዊ ነው። መንግስት ለዲያስፖራው 40/በ60ን ሲያዘጋጅ ሁለት አላማዎችን ታሳቢ አድርጎ ነው- ዲያስፖራው ጥሮ ግሮ ያገኘውን ሀብት ሰብስቦ ደቋናውን ለመሙላት እና ዲያስፖራው ስለነጻነቱ እንዳይጠይቅ ወይም መንግስትን እንዳይቃወም አፍ ለማዘጋት።

40 /በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራ እናት እና አባቱ፣ እህትና ወንድሙ፣ በአጠቃላይ የአገሩ ሰዎች ቢገደሉ፣ ቢታሰሩ ፣ ቢሰደዱ፣ ቢራቡ ፣ ቢጠሙ፣ ” ለምን?” ብሎ አደባባይ ወጥቶ የመጠየቅ እና የመቃወም ነጻነት አይኖረውም፤ ነጻነቱን በ40/በ60 ተገፎአል። ለሌላው መብት ሊሟገት ቀርቶ፣ በጥፊ ቢመታም እንኳን፣ “ጥፊው እንዴት ይጣፍጣል፣ እባክህ ግራ ጉንጨንም ድገምልኝ” ከማለት ውጭ፣ “ለምን ትመታኛለህ?’ ብሎ የአባትና እናቱን ወኔ ቀስቅሶ ብድሩን የመመለሻ ልብ አይኖረውም። እስክንድር ነጋ፣ አበበ በለው፣ ብርሀኑ ነጋ፣ እና ሌሎችም፣ ከስጋቸው ድሎት ነጻነታቸውን ያስቀደሙ በርካታ ኢትዮጵያውያን፣ ባርነት በቃን በማለታቸው፣ ጥረው ግረው ያፈሩትን ሀብት ተነጥቀዋል።
40/በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራ ስለወገኑ ለመጮህ ከእንግዲህ በአውሮፓ እና በአሜሪካ ከተሞች እጅግም አይታይም፣ ለይሉንታ ቢታይ እንኳ ፊቱን በወረቀት ሸፍኖ ከሁዋላ ከመሰለፍ የዘለለ ሚና አይኖረውም። በነጻነት አገር እየኖሩ ገንዘብ ከፍሎ፣ በፍላጎት ባርነትን መምርጥ ማለት ይህ አይደለምን? የሚገዛ የለም እንጅ እነዚህ ሰዎች እኮ መንግስት ቢሸጣቸው እንኳ ምንም የሚናገሩ አይደሉም። ገንዘብ ተከፍሎ ባሪያ አድርጉን ብሎ የሚጠየቅበት አሰራር በታሪክ ታይቶ ይታወቃልን?

በአገር ቤት ያለው ህዝብ ለ 20/በ80 ቢመዘገብ አይገርመኝም፤ በባርነት ውስጥ የሚኖር ህዝብ በመሆኑ፣ አንድ ቀን ራሱን ነጻ እስኪያወጣ፣ ለጊዜው ተመችቶት ይኑር። ባሪያም እኮ ልብሱን ይቀይራል፣ የምኝታውን ሳር ተባይ ሲወርበት በሌላ ሳር ይተካዋል፤ ባበርነት ስር ያለው የአገር ቤት ሰው በነፍሱም በስጋውም ሊበደል አይገባውም፤ ቢያንስ እስከ ጊዜው በስጋው ይደሰት። ዲያስፖራው ግን የኢትዮጵያን ምድር ከለቀቀባት ጊዜ ጀምሮ ከባርነት ነጻ ወጥቷልና በነጻነት መኖር የሚችለበት እድል አለው፤ ለራሱ ብቻ ሳይሆን ለሌላውም ነጻነት ለመታገል ሁኔታው ተመቻችቶለታል፤ ይህን ነጻነቱን ግን እራሱ ገንዘብ ከፍሎ ሊሸጠው ይደራደራል። ፍርፋሪ እየተጣለለት ወደ ቄራ የሚወሰድ እሪያ መጨረሻው ሞት እንደሆነው ሁሉ፣ 40/በ60 የተመዘገበ ዲያስፖራም መጨረሻው ባርነት ነው። አምስተኛው ባርነት!


ኢሕአፓ፣ እኔ እማውቀው፣

0
0

tower-in-the-sky-300x399(ባለፈው ሰሞን በሕይወት ተፈራ ተደርሶ ለንባብ ለበቀው፣ Tower In the Sky፣ ስለተባለው መጽሀፍ ውስጥ በተነሱ አንዳንድ ጉዳዮች ላይ የቀረበ አስተያዬት፣)
ከሰላሙ ባላይ፣

ሙሉውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

የሥላሴዎች እርግማን (ሦስት) ፦ አዳክሞ ማደህየት –ከፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

0
0

ከፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

ሐምሌ 2005

አንድ በጣም የተገረመ ደቡብ አፍሪካዊ ይህንን ሁሉ መንገድና ሕንጻ በአንድ ጊዜ ለማሠራት ገንዘቡን ከየት ነው የምታገኙት? ብሎ ጠየቀኝና ከወርቅ-ቡና አልሁት፤ ሳቅ አለና እኔኮ ከልቤ ነው የምጠይቅህ አለኝ፤ እንግዲያው ዘክዝኬ ልንገርህ አልሁት፤ ለወትሮው ብዙ የምክር ዋጋ የሚያስከፍል ቢሆንም ለመንግሥትህ እንዳትናገርና የዚሁ ዓይነት ሥራ በደቡብ አፍሪካ እንዳይጀመር ቃል ግባልኝ አልሁትና ቀጠልሁ፤ ከጥቂት ሳምንታት በፊት በመንግሥት ባንኮች ደጃፍ ላይ የነበረውን መጨናነቅ አይተሃል ወይ? ብዬ ጠይቄው ማየቱን ካረጋገጥሁ በኋላ ጉዳዩን እንደሚከተለው አስረዳሁት፡፡

Pro Mesfinአገዛዙ መሬቱንም ሆነ ቤቶችን የራሱ ካደረገና ባለቤትነቱን ካረጋገጠ በኋላ በየመንገዱ ዳር እንጀራ፣ ዳቦ፣ ቆሎ፣ ጠላና ትናንሽ ነገር እየሸጡ ልጆቻቸውን የሚያሳድጉ ሴቶች፣ በየቤቱ እየሠሩ በነዚህ ቤቶች ተዳብለው ኪራይ እየከፈሉ የሚኖሩ ሴቶች በብዛት ነበሩ፤ በነዚህ ደሀዎች ላይ ቀበሌዎች በየጊዜው እየዘመቱ ቤቱ እንደሚፈርስባቸው እያስፈራሩ ደሀዎችን ያሸብራሉ፤ በዚህ ዓይነት ፍርሃትና ስጋት ውስጥ ለጥቂት ወራት ካቆዩአቸው በኋላ ክረምትን ጠብቀው በግድ ያስለቅቁአቸዋል፤ በዚህ ምክንያት በአዲስ አበባ ውስጥ የተፈናቃይ ቁጥር በየዓመቱ እየጨመረ በአንዲት ትንሽ ክፍል ውስጥ የሚኖረው ሰው ቁጥር እየበዛ ለጤንነት ክፉ ጠንቅ እየሆነ ነው፤ ይህ ችግርና ስቃይ ትልቅ የሀብት ምንጭ ሆኖአል፤ ደሀ የሚበላው አንጂ የሚከፍለው አያጣም፤ ነጭ ደሀ ነጭ ማር ይከፍላል፤ እነዚህ ባህላዊ አነጋገሮች ተጠንተው በተግባር ላይ እየዋሉ ነው።

እንዴት? ማለት ጥሩ ነው፤ እነዚህ (ቤቶቻቸው ከማለት ይልቅ) መጠለያዎቻቸው የፈረሱባቸው ሰዎች ከረሀቡ ሌላ በብርድና በጸሐይ በመጉላላታቸው የመጠለያ ችግራቸው በጣም ከባድ ስለሆነ በቀላሉ የሚበዘበዙ ናቸው፤ ችግሩን መፍቻ የሚመስል የደሀውን ነፍስ በጉጉት ሰንገው የሚይዙበት ኮንዶሚንየም የሚባል ማቁለጭለጫም አለ፤ ደሀ ሁሉ ኮንዶ አግኝቶ የሚያልፍለት ይመስለዋል፤ ስለዚህ ሁሉም ይፈልጋል፤ ስለዚህ የኮንዶ ፈላጊው ሰልፍ በጣም ረጅም ነው፤ ስለዚህ በመስገብገብ እየተተኮሰ ዋጋው በጣም ከፍ ያለ ነው።

ማፍረስ ከመገንባት የቀለለ ቢሆንም በአዲስ አበባ የሚካሄደው አብዛኛው የመገንባት ሥራም ከማፍረሱ ሥራ የተሻለ መሆኑ በጣም ያጠራጥራል፤ እንዲያውም የማፍረሱንም ሆነ የመገንባቱን ሥራ የሚመሩት የውጭ አገር (ምናልባትም የቻይና) ሰዎች ናቸው ለማለት ያስደፍራል፤ በኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ነፍስ ውስጥ መሬት እንዳለ፣ በኢትዮጵያ የብዙ ሺህ ዓመታት ውስጥ መሬት እንዳለ፣ በኢትዮጵያ የተጋድሎ ጀግንነት ውስጥ መሬት እንዳለ፣ በኢትዮጵያ የአገር ፍቅር ውስጥ መሬት እንዳለ የውጩ አገር ሰው በምን መንገድ ሊያውቅ ይችላል? አንድ ኢትዮጵያዊ በአገሩ ውስጥ ባለው ቤት ውስጥ ምን ምን ይሠራል? አንዴት ይሠራል? በዚህ ጉዳይ ላይ የውጭ አገሩ ሰው ምንም ያህል አያውቅም፤

ስቱድዮ በወር አንድ መቶ ዘጠና አምስት ብር፣ ባለአንድ መኝታ ሁለት መቶ ሰባ አራት ብር፣ ባለሁለት መኝታ አምስት መቶ ብር እንደሚከፈል ተወስኖአል፤ ይህ ኪራይ ሁላችንም እንደምናውቀውና እንደለመድነው ዓይነት ያለ ኪራይ አይደለም፤ ልዩ ነው፤ አንዱ ልዩ የሚያደርገውም መጠለያዎቹን ሁሉ ያፈረሱትና ችግሩን የፈጠሩት ራሳቸው ኪራይ ሰብሳቢዎች መሆናቸው ነው፤ ዋናው ልዩ የሚያደርገው ግን ለኮንዶዎቹ ኪራይ መክፈል የሚጀመረው ሕንጻዎቹ ተሠርተውና አልቀው ተከራዮቹ ከገቡ በኋላ አይደለም፤ የሕንጻዎቹ ሥራ የሚጠናቀቀው ቢያነስ ከአምስት ዓመት በኋላ ሲሆን ኪራይ መክፈል የሚጀመረው ዛሬ ነው! ደሀዎች ለማይኖሩበት ቤት ኪራይ ይከፍላሉ! ማንም አላስገደዳቸውም፤ ያስገደዳቸው ደካማነታቸውና መናጢ ደሀነታቸው ነው፤ መስገብገባቸው ነው።

ከቀረበው መረጃ ተነሥተን እስቲ ትንሽ ስሌት እንሥራ፤ በአጠቃላይ በአዲስ አበባ ውስጥ ስምንት መቶ ሺህ ያህል ሰዎች ለኮንዶ ተመዝግበዋል እንበል፤ በስቱድዮ፣ በአንድ መኝታ፣ በሁለት መኝታ፣ በሦስት መኝታ በእያንዳንዳቸው የቤት ደረጃዎች ሁለት መቶ ሺህ ሰዎች ቢመዘገቡ     ከነዚህ ውስጥ ግማሽ የሚሆኑት በዝቅተኛ የደሀነት ደረጃ ላይ ቢሆኑ፣ ሢሶ የሚሆኑት ደግሞ የደሀነት መሀከለኛ ደረጃ ላይ ቢሆኑ፣ ሌሎቹ ማለትም አንድ አምስተኛ የሚሆኑት በተሻለ ደረጃ ላይ ያሉ ደሀዎች ቢሆኑ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በያመቱ የሚሰበሰበው ገንዘብ እንደሚከተለው ይሆናል፤

 

ደሀነት ሲበዘበዝ

ኮንዶ የተመዘገቡ   የወር ኪራይ በደሀነት ደረጃ የዓመት ኪራይ
ስቱድዮ

200 000

 200 000 x 195=  39 000 000

  468 000 000
1 መኝታ

200 000

200 000 x 274=  54 800 000

  657 600 000
2 መኝታ

200 000

200 000 x 500= 100 000 000

1 200 000 000
3 መኝታ

200 000

200 000 x 750= 150 000 000

1 800 000 000
ድምር 1 000 000                279 700 000 4 125 000 000

 

እንግዲህ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ከመጠለያ ማጣት ጭንቀት ለማምለጥና ያደረባቸውን የኮንዶ ጉጉት ለማሳካት ከአራት ቢልዮን ብር በላይ እየተራቡ ይገብራሉ፤ በአምስት ዓመታት ውስጥ ገና ኮንዶው ውስጥ ሳይገቡ ላባቸውን ያንጠፈጠፉበትን 20 625 000 000 ብር ይከፍላሉ ግፍ ሌላ ትርጉም የለውም።

ማፍረስም በጣም ትርፋማ ሥራ ሆነ።

በፈረሰው ላይ የሚገነባውስ? ስለኮንዶው ሕንጻ አንዳንድ ጥያቄዎችን ማንሣት በግድ ያስፈልጋል፤ አንደኛ የኮንዶው ሥራ መቼ ተጀምሮ መቼ ያልቃል? ያልቃል ሲባልስ ለመኖሪያ ብቁ የሆነ፣ በሮችና መስኮቶች ተገጥመውለት፣ ወለሉና ጣራው፣ የመታጠቢያ ቤቱ ሁሉ ተሟልቶ ነው ወይስ ባለቤት የሚሆኑት ሰዎች የሚጠብቃቸው ሥራ አለው? ሁለተኛ የኮንዶው ሕንጻ ስንት ክረምትና ስንት በጋ የሚችል ይሆናል? ሦስተኛ ኮንዶው ሰዎችን ወደከፍተኛው ፎቅ የሚያደርሳቸው ‹ሊፍት› አለ ወይስ ሰዎች በእግራቸው በደረጃ ሊወጡ ነው? ይህ ከሆነ ለሽማግሌዎችና አሮጊቶች ምን ዝግጅት ተደርጎላቸዋል? ሽማግሌዎችንና አሮጊቶችን ወደምድር ቤቱ አካባቢ ለመደልደል ታስቦአል ወይ? አራተኛ የውሀ አቅርቦቱ ምን ያህል አስተማማኝ ነው? ውሀ በሚጠፋበት ጊዜ ነዋሪዎቹ ሊጠቀሙበት የሚችሉበት የመጸዳጃ ቦታ ካልተዘጋጀ በጥቂት ጊዜ ውስጥ አካባቢው ለጤና ጠንቅ እንደሚሆን መገመት አያዳግትም፤ ‹‹የአበሻ ኑሮ›› የሚባል ነገር ያለ ይመስለኛል፤ ቡናና ጌሾ መውቀጡ፣ ብቅልና በርበሬ ማስጣቱ፣ ዶሮና በግ ማረዱ፣ አንጀራ መጋገሩ፣ ማኅበሩ፣ ለቅሶው — እነዚህና ሌሎችም ማኅበራዊ ግዴታዎች ኮንዶው ሲሠራ ታስበው ነበር ወይ?

ደሀው ራሱን በማፈራረስ፣ ይበልጡኑ በሚደኸይበት ሥራ እንዲጠመድ፣ በፍርስራሽ እንዲነግድ በምናምን ተይዞአል! የሥላሴዎች እርግማን!

የልማታዊ ጋዜጠኞች አንዝህላልነት እና የአብርሃ ደስታ እማኝነት “የኢትዮዽያውያን ህይወት በዓረብ ሀገሮች “

0
0

arab ethiopiaከነብዩ ሲራክ

ባሳለፍነው ሳምንት በሳውዲ አረቢያ ግፍ ተፈጸሞባቸው ወደ ባገር ቤት የሚሸኙ እህቶች የመኖራቸው መረጃ ደረሰኝ ። በተለይም በቅርብ እከታተላቸው የነበሩ አህቶች እንግልት በመጠቆም በዚው በፊስ ቡክ የማለዳ ወግ ዳሰሳየ ላይ አንድ መልዕክት አስላልፊ ነበር! መልዕክቱም ለልማታዊ የሃገር ቤት ጋዜጠኞች ሲሆን የመልዕክቱ ፍሬ ሃሳብ ” የምንናገረውን ማመን መቀበል አቅቷችሁ እንደ ጠላት ከምታዩን ረቡዕ ወደ ቦሌ አየር ማረፊያ ሂዱና ከፍተኛ ግፍ ተፈጸደሞባቸው ከሳውዲ ተጠርፈው ወደ ባገር የሚገቡትን የኮንትራት ሰራተኞችን ተመልክቱ !”የሚል ነበር።
ንቁ እዝነ ልቦንና ያልታደሉት ልማታዊ ጋዜጠኞች በቦታው ሄደው ከቤሩት የተመለሱትን ሻንጣ የደረደሩ እህቶች በቴሌቪዥኑ መስኮት ብልጭ አድርገው ከማጥፋታቸው ባለፈ ከሳውዲ ያለጫማና የረባ ልብስ ተደብድበውና ተደፍረው የተመለሱትን ግፉአን ሊያሳዩን እንኳ አልፈቀዱም! ጋዜጠኞቻችን አልተሳሳቱም!!! የተሳሳትኩት እኔ ነኝ!!! ያን ሰሞን “ስደት ይቅር ” ምንቴስ ሰፊ ሽፋን በየሚዲያው እየሰጡ ፣ የደበቁትን መከራችን እያሳዩ እያሉ ህዝበ አዳም ፣ ሃገሬውን ሲያስለቅሱን የከረሙት ወደ ነፍሳቸው ተመልሰዋል ብየ በማሰቤ ስህተቱ የእኔ ግምት ነው!!! ጉዳታችን እዩት ቀሪው እንዲማርበት ፣ ሃላፊዎቻችን ይዩትና ወደ ዘነጉት የዜጎች ጉዳይ ያተኩሩ ዘንድ የተገፊ ግፉአኑን ጉዳይ ተከታትየ መጠቆሜ በአደባባይ ቃል የገቡትን ይፈጽማሉ ብየ በማሰቤ የተሳሳትኩት እኔ ነኝ!!! ስህተቴ አንድና አንድ ነው!!! የአረብ ሃገሩን የስደት መከራ የሚፈልጉት ለፕሮፖጋንዳ እንጅ ቀሪውን ማስተማርን እንደልሆነ አለማሰቤ ነው ስህተቴ ! በእንዝህላል ልማታዊ ጋዜጠኞቻችን አዝኘም ብቻ ሳይሆን አፍሬ ዝም ማለቴ ግን እውነት ነው! ዛሬ ማለዳ ግን መልካም መረጃም የሚየ ስፈነጥዝ ባይሆንም መረጃው በመሰራጨቱ የተደሰትኩበትን መጣጥፍ ተመለከትኩ ።
ሮብ ነሓሴ 15, 2005 ዓም ከአረብ ሃገር ወደ ሃገር የገቡትን እህቶች አብርሃ ደስታ አግኝቷ እንዳነጋገራቸው በማህበራዊ ድህረ ገጽ ካስተላለፈው መልዕክት ለመረዳት በመቻሌ ደስ አለኝ ! በገዥው የኢህአዴግ መንግስት አስተዳደር ላይ በተለይም ስለ ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ከመቀሌ ሆኖ በሚያሰራጫቸው የሰሉ ሚዛናዊ ሂሶች ተወዳጅነትን እያተረፈ የመጣው አብርሃ ድስታ ግፉአን እህቶቸችን ቦሌ አየር ማረፊያ አግኝቷቸው ያየውን የሰማውን እጥር ምጥን ባለው የለመድነው መረጃ አቀባበል እንካችሁ ብሎናል ። የአብርሃ እማኝነት አስደስቶኝ እኔም ለዛሬ ወግ ዳሰሳ አበቃሁት ! ወዳጃችን አብርሃ ደስታ ሆይ ! የአረብ ሃገሩ የብዙሃን የኮንትራት ሰራተኞች አስከፊ ህይዎት ያጫዎቱህ ወደ ሃገር ለመግባት የታደሉት መሆናቸውን አስረግጨ እነግርሃለሁ ! ያየሃቸው የታደሉት ጥቂት ምሳሌዎች ናቸው ! የመንግስት ተወካይ አለን ለማለት አልደፍርም ! እውነቱ ይህ ነው ! አንተም እንኳን ከግፉአኑ ሰምተህ አሰማህን ! ይህ የማናችንም ሃላፊነት መሆን ሲገባው እያደረግነው አይደለም! የእህቶቻችን ህይዎት በአረብ ሃገር ምስክርነቱ ይህ ነው ! እንዲህ ይኖራል ! የእኔን በዚህ ላብቃና እጥር ምጥን ወዳለችው የአብርሃ ደስታን እማኝነት ከዚህ በታች እንድትመለከቱ ስጋብዝ ለአብርሃ ምስጋና በማቅረብ ጭምር ነው! እነጰ አበቃሁ ! ቸረወ ያሰማን !
ነቢዩ ሲራከ
Abrham Desta By Abraha Desta የኢትዮዽያውያን ህይወት በዓረብ ሀገሮች ——————————————— ሮብ ነሓሴ 15, 2005 ዓም ጠዋት ቦሌ ኤርፖርት ነበርኩ። ኢንተርናሽናል ተርሚናሉ ከዓረብ ሀገራት በተመለሱ እንስት ኢትዮዽያውያን ተጥለቅልቋል። የተከፉና የተረበሹ ይመስላሉ። ከሰዓት በኋላ ወደ መቐለ ለመመለስ ወደ ሀገር ውስጥ ተርሚናል ገባሁ። ከነዚህ ጠዋት ረጅም ሰልፍ ይዘው ያየኋቸው ተመላሾች የተወሰኑ አገኘሁ። ስለ ህይወታቸው፣ ስለሚደርስባቸው እንግልት ወዘተ አጫወቱኝ። በዓረብ ሀገሮች የሚኖሩ ኢትዮዽያውያን እንደሰው አይቆጠሩም፤ ብዙ አካላዊና ስነ አእምራዊ ችግር ይደርሳቸዋል። ብዙዎቹ አብደዋል፣ ራሳቸው አጥፍተዋል። ኢትዮዽያውያን በመሆናቸው ራሳቸው ይረግማሉ፤ በመፈጠራቸው ያዝናሉ። የኢትዮዽያ ኤምባሲ ግን ምንድነው የሚሰራው? የዜጎች ደህንነት መጠበቅ’ኮ የመንግስት ሐላፊነት ነው። የኢትዮዽያውያን ስደትና ግፍ ሀገራችን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ሊመራት ይችላል።

የመለስ ዜናዊ “የሁለት አሐዝ ዕድገት” እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ኑሮ ***

0
0

ከበፍቃዱ ዘ ኃይሉ

“ለ7 ዓመታት በተከታታይ 11·6 በመቶ አድጓል” የተባለው የመለስ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ፥ የዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍም ከመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በሚገኘው መረጃ ላይ ቢመሠረቱም “የለም፤ ከ6 እስከ 8 በመቶ ነው ያደገው፣ ቢሆንም ቀሽት ነው” ይላሉ።

“ኢኮኖሚው ሲመነደግ” የሕዝቦች ኑሮ ደረጃስ እንዴት ነው?

ኢትዮጵያ በየአረብ አገራቱ የቤት ሠራተኛ አቅራቢነት ከፍተኛ ደረጃ የደረሰችው በመለስ ዘመን ነው። (ለምሳሌ አሁን ኢትዮጵያውያንን አልቀበልም ያለችውን ሳውዲ አረቢያ የቤት ሠራተኛ ፍላጎት 10 በመቶ ኢትዮጵያ ትሸፍን ነበር።) በየአረብ አገራቱ የኢትዮጵያውያን ስም ከሌብነት እና ሴተኛ አዳሪነትጋ የተያያዘ ነው።

ethiopia-famine
ከኢትዮጵያ ውጪ መውጣት ለሁሉም ዜጋ ቢፈቀድ ዐሥር ሚሊዮን ሰው እንኳን ይቀራል ብዬ መገመት ይከብደኛል። ከተሜውም ገጠሬውም ወደቻለው ቦታ ይፈልሳል። የተማረውም፣ ያልተማረውም ኢኮኖሚያዊ ስደትን የመምረጡ እውነት የኢኮኖሚያዊ ዕድገቱን እውነተኝነት ጥያቄ ምልክት ውስጥ ይከተዋል።

የመሠረተ ልማት ግንባታዎች በተለይ የመንገድ ሥራዎች ሲነቃቁ የግሉ ዘርፍ (ከኢሕአዴግ “የኢንዶውመንት” ቢዝነሶች በቀር) ተዳክሟል። ያሉትም የግል ቢዝነሶች ቢሆኑ በፖለቲካ ጥቅም የሚለመልሙ በመሆናቸው በከተሞች መሐል የሚበቅሉ ብልጭልጭ ሕንፃዎች የሙስና ሲሳይ ናቸው። ከሕንፃዎቹ ጀርባ ያሉት ያው የድሮዎቹ ቆሼ ሰፈሮች ናቸው። እንደ HDI ያሉ የUN የሰብኣዊ ልማት መለኪያዎችም የሚያሳዩን ኢትዮጵያውያን ዛሬም በድህነት እየማቀቁ መሆኑን ነው።

“ስኳር የተወደደው ድሃው ስኳር መብላት ጀምሮ ነው” ያሉት መለስ ስኳሩን የሚልሱት እነማን እንደሆኑ እንኳ ሳይረዱ ያለፉ ይመስለኛል።

አቶ መለስ ምንጩንና መጠኑን ማንም ያልገመተው፣ የባለብዙ ሀብት ባለቤት፣ የትዳር አጋራቸውን ጨምሮ ሌሎች ጥቂት ሀብታሞች ያሉበት የጥቅመኞች ክበብ እየዳጎሰ ብዙኃኑ የሚቀጭጩበትን የቢዝነስ ስርዓት በመፍጠር በቁጥር ጫወታ አድጋችኋል ይሉናል። ድሃ ተኮር ፖሊሲ ቀርጫለሁ፣ ለልማቱ ብዬ ነው ዴሞክራሲን የበደልኩት ብለው ያተረፉልን ነገር ቢኖር አገርክን ጥለህ ብረር፣ ብረር የሚያሰኘው ምስኪን፣ ድሀ ትውልድ ብቻ ነው።

ሕዝባዊ ስብሰባ በሲያትል በአካባቢው ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live