Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ኤልያስ ክፍሌ ይቅርታ ጠየቀ –“ከሻዕቢያ ጋር እንስራ ብዬ መቀስቀሴ ስህተት ነበር” (Video)

$
0
0

ሰሞኑን አነጋጋሪ ሆኖ በየስፍራው ስሙ እየተጠራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሪቭው ድረገጽ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ኤሊያስ ክፍሌ ይቅርታ ጠየቀ:: ኤሊያስ ሰሞኑን በዋሽንግተን ዲሲ በተጠራ ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ባደረገው ንግግር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ምላሽም ሰጥቷል:: ሙሉውን ቭዲዮ ይመልከቱት::

ኤልያስ ክፍሌ ይቅርታ ጠየቀ – “ከሻዕቢያ ጋር እንስራ ብዬ መቀስቀሴ ስህተት ነበር”

Youtube Link >>>>

↧

↧

አርበኞች ግንቦት 7 ጥቃት መፈጸም ከጀመረ ወዲህ የወልቃይት ሕዝብ በስርዓቱ አንገዛም ብሎ በአንድነት መነሳቱ ተዘገበ

$
0
0

ESAT
አርበኞች ግንቦት 7 ራድዮ እንደዘገበው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ስርዓት ክልል 1 እና ክልል ሦስት ብሎ የከፈለው የወልቃይት ህዝብ በስርዓቱ አንገዛም ብሎ በአንድነት ተነስቷል፡፡

የወልቃይት ህዝብ “ክልል 1 እና ክልል 3 የሚባል አናውቅም እኛ የጎንደር በጌ ምድር ተወላጆች ኢትዮጵያዊያን ነን” ሲል በአንድነት “ሆ” ብሎ በመነሳት ከእንግዲህ ወዲህ ህወሓት በዘረጋው የፌደራሊዝም ጭምብል ያጠለቀ የጎሳ አስተዳደር እንደማይመራ እንደ ብረት የጠነከረ አቋሙን በመግለፅ ላይ ነው፡፡

የወልቃይት ህዝብ እስካሁንም ድረስ እትብቱ የተቀበረበት መሬቱ ከሁለት ተሰንጥቆ ከፊሉ ክልል 1 ከፊሉ ደግሞ ክልል 3 ተብሎ በህወሓት ዘረኛ ቡድን መቆረሱንና አንድነቱን ሸርሽሮ ለማዳከም የተቀነባበረውን ስውር ደባ እጆቹን በማጣጠፍ ቆሞ አልተመለከተም ነበር፡፡

ከ1992 ዓ.ም አንስቶ እልህ አስጨራሽ ትግል በማድረግ ከፍተኛ መሰዋዕትነት ሲከፍል ኖሯል፡፡ ዘረኛው የህወሓት ቡድን የወለቃይትን የአንድነትና የነፃነት ጥያቄ ያነሱትን ልጆቹን በየጊዜው በመረሸን ህዝቡንም በጅምላ መጨፍጨፍና ዘር በማጥፋት ጥያቄውን በኃይል አዳፍኖት ሊቀር ብዙ ጥረት አድርጓል፡፡

ነገር ግን ዛሬ ህወሓት በወልቃይት መሬት ላይ ያዳፈነው ረመጥ ውስጥ ለውስጥ ሲቀጣጠል ቆይቶ ሳያስብው ግር ብሎ ነዶ ራሱን እየለበለበው ነው፡፡

በህወሓት የዘር አገዛዝ በእጅጉ የተማረረው የግፍና በደል ገፈትን ሲጎነጭ የኖረው የወልቃይት ህዝብ የህቡና ይፋዊ አስተባባሪ ኮሚቴዎቹን በመምረጥ በሚገባ ተደራጅቶ ህወሓትን በማንኛውም መስክ ሊፋለመው በአንድነት ተነስቷል፡፡
በመሆኑም ከአዲ ረመፅ 3፣ ከጠገዴ 3 እና ከቃፍታ 1 በድምሩ 7 ይፋዊ ኮሚቴዎችን መርጦ “ክልል 1 እና ክልል 3 አላውቅም፤ እኔ የጎንደር በጌምድር ኢትዮጵያዊ ነኝ” በማለት ከእንግዲህ ወዲህ የህወሓትን የጎሳ አስተዳደር ፈፅሞ የማይቀበለው መሆኑን እንዲያስታውቁለት ወደ አዲስ አበባ ልኳል፡፡

↧

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቴዲ አፍሮ ምክንያት 200 ሺህ ዶላር ከሰረ * ቴዲ በድጋሚ ፓስፖርቱን ተቀምቶ ነበር

$
0
0

· ቴዲ በድጋሚ ፓስፖርቱን ተቀምቶ ነበር

(ክንፉ አሰፋ፣ ፍራንክፈርት) ባለፈው ሳምንት ወደ ከአዲስ አበባ ናይሮቢ-ኬንያ ይጓዝ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራውን ከጀመረ በኋላ እንዲመለስ መደረጉን የአየር መንገዱ ምንጮች አስታወቁ። በዚህም ምክንያት አየር መንገዱ የሁለት መቶ ሺህ ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ምንጮቹ ጠቁመዋል። በተሳፋሪዎች ላይም ከፍተኛ መጉላላት ደርስዋል።
teddy afro
አውሮፕላኑ ካኮበኮበ በኋላ እንዲመለስ የተደረገበት ምክንያት ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ ከባለቤቱ ከአለምሰት ሙጬ ጋር በአውሮፕላኑ በመሳፈሩ ምክንያት መሆኑ ተረጋግጧል። ይህ አስደንጋጭ ክስተት የተፈጸመው አለምሰት ሙጬ በደረሰባት ድንገተኛ ህመም ለህክምና ወደ ኬንያ እየተጓዘች ባለችበት አውሮፕላን ነው።

አውሮፕላኑ ዞሮ ከተመለሰ በኋላም ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ በደህንነቶች ተይዞ ከአውሮፕላኑ እንዲወጣ ተደርጓል። የህወሃት የደህንነት አባላት የቴዲ አፍሮን ፓስፖርት ቀምተው አሰናብተውት ነበር።

ቴዲ አፍሮ በሰሜን አሜሪካ በየዓመቱ የሚደረገው የኢትዮጵያውያን የስፖርት እና የባህል ፌስቲቫል ላይ ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ ጋር መጋበዙ የሚታወስ ሲሆን ይህንን በመቃወም ሚሚ ስብሃቱ እና ባለቤትዋ ዘሪሁን ተሾመ ዘመቻ ከፍተው እንደነበር የሚታወስ ነው። የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን 33ኛ ዓመት በዓል ላይ እነዚህ ድምጻውያን አልተገኙም። ድምጻውያኑ በበዓሉ ያልተገኙበት ምክንያት የአሜሪካ ኤምባሲ ላይ በደረሰው የኮምፒውተር ሽብር ጥቃት- የቪዛ ችግር ያጋጠማቸው መሆኑ ቢገለጽም፤ ቪዛ ቢያገኙ ኖሮ እንኳ በደህንነቶች አፈና ከሃገር ሊወጡ እንደማይችሉ ግልጽ ነበር።

የኢትዮጵያውያን የስፖርት እና የባህል ፌዴሬሽን አሸባሪ ተብሎ በነሚሚ ስብሃቱ መፈረጁን የህወህት መንግስት ተቀብሎ በውስጥ አጽድቆታል። ቴዲ አፍሮ ባለቤቱን ለማሳከም ወደ ኬንያ በመጓዝ ላይ እንዳለ በኬንያ በኩል ወደ አሜሪካ ሊጓዝ ነው ተብሎ በነ ሚሚ ስብሃቱ በደረሰው ጥቆማ ነው አውሮፕላኑ እንዲመለስ የታዘዘው። በዚህ በተሳሳተ መረጃ ምክንያት በተሳፋሪው ላይም ከፍተኛ መጉላላት የደረሰ ሲሆን አየር መንገዱም ለከፋ ኪሳራ ተዳርጓል ሲሉ የአየር መንገዱ ምንጮች ተናግረዋል። ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ ከባለቤት ጋር ወደ ኬንያ ይጓዝ የነበረው የሰሜን አሜሪካው የስፖርት እና የባህል ፌስቲቫል ከተጠናቀቀ በኋላ ነበር። የህወሃት ደህንነት አባላት ይህንን እንኳን ማገናዘብ የማይችሉ ደካሞች እንደሆኑ ምንጮቹ ተቁመዋል።

ከብዙ መጉላላት በኋላ ቴዲ አፍሮ ፓስፖርቱን አስመልሶ ወደ ጀርመን – ፍራንክፈርት የበረረ ሲሆን በቅዳሜ ምሽት የአውሮፓ ስፖርትና ባህል ፌስቲቫል ላይ ዝግጅቱን ያቀርባል። ከዚያም የጄኔቭ ስዊዘርላንድ ማዘጋጃ ባሰናዳው ዝግጅት ላይ ልዩ ተጋባዥ በመሆን በመጭው ሳምንት ስራውን ለህዝብ በነጻ ያሳያል።

የቴዲ አፍሮ ባለቤት አለምሸት ሙጬ በአሁኑ ሰዓት በአሜሪካ-ቨርጂንያ ህክምናዋን እየተከታተለች ትገኛለች።
ድምጻዊ ቴዲ አፍሮን በአካል አግኝቼ ባነጋገርኩበት ግዜ የዚህን ዘገባ ትክክለኝነት አረጋግጫለሁ። ይህንን እጅግ አሳሳቢ ጉዳይ ወደፊት በስፋት እመለስበታለሁ።

↧

በካናዳ ጀርመናዊው የገደላት ሰብለ ከአንድ አመት በኋላ በመኖርያ ቤቷ ተቀብራ ተገኘች

$
0
0

(ክንፉ አሰፋ ቶሮንቶ) ሰብለ (ሚሚ) ዲትሪች ለመጨረሻ ግዜ የታየችው እ.ኤ. አ. ጁላይ 10 2014 (ባለፈው አመት) ነበር። የሶስት ልጆች እናት የነበረች የዚህች ኢትዮጵያዊት በድንገት መሰወር ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኖ ሰንብቷል። ለአመት የጠፋችው ይህች ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሴት በህይወት እንደማትኖር በርካቶች ቢጠረጥሩም፣ ማንንም ሳታማክር በድብቅ ወደ ሃገርዋ ገብታለች የሚሉ አልጠፉም። አለም አቀፍ ፖሊስ በአለም ዙርያ ፍለጋውን ተያያዘው።
ሰብለ-ቀብር

ሰብለ
በካናዳ ኪችነር ከተማ ቫንኮቨር ድራይቭ የተገኘው አጽም ግን የሁሉንም እንቆቅልሽ ፈታው። ሰብለ ህይወትዋ አልፏል። የሶስት ልጆችዋ አባት የነበረው ጀርመናዊው ስቴፋን ዲትሪች ገድሎ እዚያው መኖርያ ቤታቸው እንደቀበራት ፖሊስ ጠቁሟል። በፖሊስ እና በሰለጠኑ ውሾች ጥቆማ የተገኘው የሰብለ አስከሬን በቶሮንቶ ኮርነርስ ኮምፕለክስ ለጥናት ተልኮ የተገኘው ውጤት ሰብለ በሰው እንደተገደለች ተረጋግጧል። ዋናው ተጠርጣሪም ጀርመናዊው ባለበትዋ ነው።

በመጀመርያ ደረጃ የግድያ ወንጀል የተከሰሰው የሚሚ ባለቤት ስቴፋን ዲትሪች ፍርድ ቤት ቀርቦ በሰጠው ቃል ጉዳዩ በጀርመን ሃገር እንዲታይለት ጠይቋል። በእለቱ ኢትዮጵያውያን ፍርድ ቤቱን አጥለቅልቀውት ነበር።
ሰብለ ዲትሪች ተገድላ ከተሰወረች ከአመት በኋላ የቀብር ስርዓትዋ እለተ አርብ (ጁላይ 18) በካናዳ ቅዱስ ፓውሎስ ቤተ ክርስትያን ተፈጽሟል። በቀብሩ ላይ ወላጅ እናትዋን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል።

ስቴፋን ዲትሪች የአዞ እንባ እያነባ ምስጢሩን ለአመት ከደበቀው በኋላ መኖርያ ቤቱን ለመሸጥ ማስታወቅያ አውጥቶ ነበር። ይህ ድርጊቱ የፖሊስን ጥርጣሬ እንዳጎላው ግልጽ ነው።

ሰብለ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ነበረች። የቤተ ክርስትያኑ ዘማሪም ናት። ባልዋ ዲትሪችም እንደዚሁ። ከጀርመን ሃገር ወደ ካናዳ ከተዘዋወሩ በሁዋላ እጅግ በጣም የተደላደለ ኑሮ እንደነበራቸው ይነገራል። ሰብለ ከኢትዮጵያውያን የቤተ-ክርስትያን ሰዎች በተለይ ከፓስተሮች ጋር የምታደርገው የአገልግሎት ግንኙነት ግን ለስቴፋን ዲትሪች እንዳልተመቸው የሚመሰክሩ አሉ። ይህም ቢሆን ክቡር ነብስን ለማጥፋት ምክንያት ሊሆን አይችልም። …. ስቴፋን ዲትሪች ሰብለን ለምን ገደላት? ገድሎስ ለምን ቤቱ ቀበራት? ይህንን ከፍርድ ቤቱ ሂደት የምናየው ይሆናል።
የሰብለ እናት የካናዳ የመኖርያ ፈቃድ አግኝተው የመጡ ሲሆን ሶስት ልጆቹን እሳቸው እንደሚንከባከቧቸው ከካናዳ መንግስት መረጃ አግኝቻለሁ።

↧

አርበኞች ግንቦት 7 በወልቃይትና አርማጭሆ መሬቶች ላይ እየተደረገ የሚገኘው ጦርነት በህዝቡና በህወሓት መካከል ሆኗል አለ

$
0
0

arebegnoch
የአርበኞች ግንቦት 7 ራድዮ እንደዘገበው:

* ‪‎የተጀመረው‬ የነፃነት ትግል በኢትዮጵያ መሬት ላይ በህዝቡ መካከል ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
* የህወሓት‬ አገዛዝ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ሲፈፅመው የቆየው እስር፣ አፈና፣ ግድያ፣ ማንገላታት፣ ማሸበርና ማፈናቀል በነፍጥ የሚደረገው ትግል ከተጀመረ ወዲህ በእጅጉ ከፍቷል፡፡

ሁለገብ የትግል ስልት የሚከተለው አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ በጠብመንጃ ስልጣን ጨብጦ በመንግስትነት ስም የኢትዮጵያን ህዝብ አፍኖ እየገዛ እና አንጡራ ሀብቱን ከገደብ በላይ እየመዘበረ የሚገኘውን ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ የተባለ ዘረኛ ቡድን ከመመካትም አልፎ በሚያመልከው ጠብመንጃ ደምስሶ በምትኩ ህዝባዊ መንግስት እንዲመሰረት ለማድረግ በበረሃ የጀመረው የትጥቅ ትግል በኢትዮጵያ መሬት ላይ በህዝቡ መካከል አንድ እግሩን በአስተማማኝ ሁኔታ ተክሏል፡፡
መላ ኢትዮጵያን ከጫፍ እስከ ጫፍ በሸፈነ መልኩ በቅርቡ ለሚደረገው የህወሓትን ጎጠኛ ቡድን በኃይል ጠራርጎ ከአገራችን ምድር የማስወገድ ጦርነት የነፃነት ትሉ ብቸኛ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ሙሉ በሙሉ እንዲሳተፍ እና በበላይነት እንዲመራው የሚያስችሉ ህወሃትን ህልውና በማሳጣት ግብአተ መሬቱን የሚያፋጥኑ ሰፊና ጥልቅ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው፡፡

ሰኔ 25 2007 ዓ.ም በወልቃይት የተጀመረው ህወሓትን የማድማትና ከስሩ የመገዝገዙ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ወደ አርማጭሆ ተስፋፍቶ ህዝባዊነትን በተላበሰ ሁኔታ የማውደም ስልቱን እየቀያየረ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

አርበኞች ግንቦት 7 ሉኣላዊ የስልጣን ባለቤት እንዲሆን የሚታገልለት የኢትዮጵያ ህዝብም የትግሉ ባለቤትና መሪ ሊሆን የሚችልበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥራል፡፡ በመሆኑም በአሁኑ ወቅት በወልቃይትና አርማጭሆ መሬቶች ላይ እየተደረገ የሚገኘው ጦርነት በህዝቡና በህወሓት መካከል ሆኗል፡፡ በአካባቢው ህወሓት ሲያደርሰው በቆየው ግፍና በደል ተማረው ከፋኝ ብለው ነፍጥ በማንሳት ጫካ ገብተው የሸፈቱት ገበሬዎች በአርበኞች ግንቦት 7 ጥላ ስር በአንድነት እየተሰባሰቡና በአንድ ዓላማ ተሳስረው የነፃነት ፍልሚያውን አጋግለውት ይገኛሉ፡፡ ህወሃት መራሹ የመከላከያ ሰራዊት በያቅጣጫው በሚደርስበት የደፈጣ እና ድንገተኛ ጥቃት መድረሻው ጠፍቶበት እየታመሰ ይገኛል፡፡ በሰራዊቱ መካከል እርስበርስ አለመተማመን እያየለ ከመምጣቱ በተጨማሪ ሽሽትና መክዳት የዕለት ከዕለት ተግባሩ ሆኗል፡፡

በመላው ኢትዮጵያ ብልጭ ድርግም ሲል የቆየው የፀረ ህወሓት ትግል ንቅናቄ ችቦ ተለኩሶ መንቀልቀል በመጀመሩ ህዝቡ በየአካባቢው ያለማንም አነሳሽ በራሱ ውስጥ ለውስጥ እየተደራጀ ለአይቀሬውና የመጨረሻው ፍልሚያ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡

አርበኞች ግንቦት 7 በህወሓት ላይ ወታደራዊ እርምጃ መውሰድ ከጀመረ ወዲህ ቁጥር ስፍር የሌላቸው ወጣቶች የትጥቅ ትግሉን በመቀላቀል ላይ ናቸው፡፡ ከአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ የእንቀላቀል ጥያቄ የሚያቀርቡ ኢትዮጵያዊያን ቁጥር በጅጉ በመጨመሩ አርበኞች ግንቦት 7 አዳዲስ ታጋዮችን የመቀበሉ ተግባር ከአቅሙ በላይ እየሆነበት መጥቷል፡፡
አርበኞች ግንቦት 7 በኢትዮጵያ መሬት ላይ በህዝቡ መካከል እያደረገ ከሚገኘው ጦርነት ጎን ለጎን ከመተማ እስከ ጎጃም እንዲሁም አርባ ምንጭ ድረስ የድርጅቱን ህዝባዊ ዓላማና የትግል ጥሪ የያዙ በራሪ ወረቀቶችን አሰራጭቷል፡፡

የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ቡድን በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ለ24 ዓመታት ሲፈፅመው የቆየውን መጠነ ሰፊ ሽብር አሁንም በተለይም ደግሞ አርበኞች ግንቦት 7 እርምጃ መውሰዱን ተከትሎ በከፋ ሁኔታ አጠናክሮ ቀጥሎበት ይገኛል፡፡

ህወሓት በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ታማኝ የሚላቸውን ደህንነቶቹንና የታጠቁ ቡድኖቹን አሰማርቶ ህዝቡን በተለይም ደግሞ ወጣቶችን እያፈነ ወደ ስውር ማጎሪያው በመውሰድና ሰቆቃ በመፈፀም ተግባር ከመጠመዱ አልፎ ሌላ ጭምብል በማጥለቅ ህዝብ ጨፍጭፎ የህዝብ ድጋፍ ለማግኘት ስውር ሴራ መጠንሰሱን ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት ቢሮ አፈትልኮ የወጣው መረጃ አጋልጧል፡፡

ከህወሓት የደህንነት ቢሮ ታማኝ ምንጮች የተገኘው መረጃ እንደሚያረጋግጠው ህወሓት በጎንደርና አካባቢው በጦር አውሮፕላን ህዝብ በመጨፍጨፍ በአርበኞች ግንቦት 7 እና በኤርትራ መንግስት የማላከክ ስውር ዕቅድ ነድፎ አሳቻ ሰዓት እስኪያገኝ እየተጠባበቀ አድብቶ ይገኛል፡፡

↧
↧

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ምክትል አሰልጣኝ አሊ ረዲ በጀርመን ከ3600 ዶላር በላይ ተዘረፈ

$
0
0

* ዘራፊው ፓስፖርቱን መልሷል!
ኢትዮኪክ እንደዘገበው በጀርመን – ፍራንክፈርት የአውሮፖ የኢትዮጵያኖች የስፖርት እና ባህል ፌስቲቫል ላይ ከኢትዮጵያ ለተወከለው “የአበበ ቢቂላ” ቡድን የተጫወተው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ አሊ ረዲ ትላንት የገንዘብ እና ፖስፖርቱን የያዘበት ቦርሳ ጠፍቷል።
ጀርመን ፍራንክፈርት ከገባ ጀምሮ ከሆቴል ውጭ ከአሊ ተለይቶ የማያውቀው መለስተኛ ቦርሳ ትላንት በድንገት የፌስቲቫሉ ዝግጅት በሚካሄድበት ስፍራ ላይ በውስጡ 3600 የአሜሪካን ዶላር ከ900 ኤውሮ እና ከፓስፖርቱ ጋር ጠፍቷል።
በፌስቲቫሉ ስፍራ አሊ ረዲን ዛሬ አግኝተነው ስለ ጉዳዮ ጠይቀነው ሲመልስ ቦርሳውን በምን እና የት ቦታ ላይ ከጀርባው አውርዶ ይህ አጋጣሚ እንዴት እንደተፈጠረ ማስታወስ አለማቻሉን ጠቁሞ ይሁንና ገንዘቡን የወሰደው ግለሰብ ፓስፖርቱ መሬት ላይ ወርውሮት መገኘቱን ለኢትዮ ኪክ ተኗግሯል።
የአሊ ረዲ የገንዘብ መጥፋት ተከትሎ ከኢትዯጵያ አብረውት የተጓዙት እና በውድድሩ ላይ ከአንደኛ ዲቪዚዮን ለዋንጫ ፍፃሜ ደርሰው ዋንጫውን ባይሳኩም በሁለተኝነት ወደ ዋናው ዲቪዚዮን ያለፉት የአበበ ቢቂላ ቡድን ተጨዋቾች ለአሊ ጥቂት ገንዘብ ማዋጣቸው ተሰምቷል።asletagne

↧

ሰበር ዜና :- ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ አስመራ ገቡ

$
0
0

Birhanu Nega

ከዚህ ቀደም ዘ-ሃበሻ ሊሄዱነው ብላ በዘገበችው መሰረት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ አስመራ መግባታችው ተረጋገጠ ዶክተሩ ወደ አስመራ የሄዱት አርበኞች ግንቦት 7 ሰሞኑን ጦርነት በህውሃት መንግስት ላይ መክፈቱን ተከትሎ ነው ::

ዝርዝሩን ወደ በኋላ እንመለስበታለን

↧

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎች የግንቦት 7 አመራሮች አስመራ ገቡ (ዝርዝር ዘገባ)

$
0
0

Birhanu Nega Breaking news
(ዘ-ሐበሻ) የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ከሌሎች የግንቦት 7 አመራሮች ጋር በመሆን አስመራ መግባታቸውን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አረጋገጡ:: ከዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ጋር አቶ ነአምን ዘለቀም ተጉዘዋል እየተባለ ሲሆን ዘ-ሐበሻ ይህን በማጣራት ላይ ትገኛለች::

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ባለፈው ጁላይ 3 በዋሽንግተን ዲስ “ካሁን በኋላ ሕዝብን ሰብስቦ ማነጋገር ላቆም ነው” ማለታቸውን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም::

የአርበኞች ግንቦት 7 ሰሞኑን የሕወሓት መንግስት ከትግራይ ክልል ጋር በግድ ቀላቀለው በሚባለው ወልቃይት አካባቢ ጥቃት ማድረሱን እና እስካሁንም ከ100 በላይ የሕወሓት መንግስት ወታደሮችን መገድሉን ሲያሳውቅ ከርሟል::

ከሰሞኑ እየተቀጣጠለ ያለው ትግል መድረሻውን አራት ኪሎ ቤተመንግስት ለማድረስ ነው ሲል አርበኞች ግንቦት 7 በተደጋጋሚ ሲገልጽ የቆየ ሲሆን ዶ/ር ብርሃኑ ነጋም ሆነ ሌሎች የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር አባላት የሕይወት መስእዋትነት ሳይቀር ለመክፈል ወደ ትግሉ ሜዳ መውረዳቸውን ከንቅናቄው አካባቢ ዘ-ሐበሻ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል::

ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ አስመራ ሊሄዱ ነው ስትል መዘግቧ የሚታወስ ሲሆን በዚህም መሠረት ዶ/ሩ ትናንት ማምሻውን አስመራ መድረሳቸውን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አርጋግጠዋል::

ሜዳ ላይ ሕይወታቸውን ለመስጠት የተዘጋጁት የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት አባላት የመሪዎቹ ድጋፍ ስለሚያስፈልገው ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደዚያው ሄደዋል:: ዶ/ሩ ወደ አስመራ ከመሄዳቸው አስቀድሞ በዋሽንግተን ዲሲ ከሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የተሰባሰበውን የመድሃኒትና ሌሎች ቁሳቁሶችን መረከባቸውን ዘ-ሐበሻ ዘግባ ነበር::

ከዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ጋር የንቅናቄው አመራር አባል የሆኑት አቶ ነአምን ዘለቀም ተጉዘዋል የሚሉ መረጃዎች ለዘ-ሐበሻ የመጡ ሲሆን ጉዳዩን ለማጣራት ወደ አቶ ነአምን ዘለቀ የሰሜን አሜሪካ ስልክ ስንደውል ስልካቸው ዝግ መሆኑን ለማረጋገጥ ችለናል:: 100% አስመራ ሄደዋል የሚለውን ለማረጋገጥም ዘ-ሐበሻ እየሰራች ትገኛለች::

የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ ትግሉ ሜዳ መውረድ ትግሉን የበለጠ ያፋፍመዋል የሚሉ የፖለቲካ ተንታኞች አሉ:: በተለይም ‘አሜሪካ ሆኖ መታገል አይቻልም” ለሚሉት ትችቶች ትክክለኛ ምላሽ ነው የሚሉ ተንታኞችም አሉ::

በዚህ ዙሪያ ዘ-ሐበሻ ተከታታይ መረጃዎችን ትለቃለች::

↧

ሠራዊቱ በሕወሓት ሰዎች ላይ እርምጃ መውሰድ ጀምሯል * በአዲሃገራይ አንድ ወታደር 3 ኮለኔሎችንና ወታደሮችን ገድሎ ራሱን አጠፋ

$
0
0

clash
የትህዴን ድምጽ ራድዮ እንዘገበው በአዲ ሃገራይ አካባቢ የሚገኝ ለግዜው ስሙ ያልታወቀው ወታደር 3ት ኮለኔሎችና ሌሎች በርከት ያሉት ወታደሮች በመግደል ራሱን እንዳጠፋ ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ገለጸ። ራድዮኑ ከሰሜን የደረሰን መረጃ እንዳስረዳው ሲል በዘገበው ዘገባው- በገዢው የኢህአዴግ ስርአት መከላከያ ሰራዊት ውስጥ ታስረው የሚገኙ ወታደሮች የሰራዊቱ ከፍተኛ አዛዦች በሚከተሉት ከፋፋይ አሰራር ምክንያት ተማርረው የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰዱ መሆናቸውን የገለጸው መረጃው አሁንም በአዲ ሃገራይ አንድ ወታደር ለ3ት ኮነሬሎች ከነ አጃቢዎቻቸው በኡርምታ ቶክስ በመግደል ለራሱም ህይወቱን እንዳጠፋ ለማወቅ ተችሏል።

ይህ በያዝነው ሳምንት በ3ት የኢህአዴግ ኮነሬሎች ላይ የተውሰደው እርምጃ ለብዙዎቹ በላያቸው ልይ ግፍ ሲፈፀምባቸው የነበሩ ወታደሮች እርካታ የሰጠ መሆኑና ሌሎች አዛዦችም በላያቸው ላይ ተመሳሳይ እርምጃ እንዳይወሰድባቸው ስጋት መግባታቸውን የተገኘው መረጃ አክሎ አስረድቷል ሲል የትህዴን ራድዮ ዘገባውን ቋጭቷል::

↧
↧

“ዝግጅቱ የህወሓት ፌስቲቫል እንጂ የኢትዮጵያዊያን አልነበረም”

$
0
0

AESAONE

ከካሳሁን ይልማ (የኢሳት ጋዜጠኛ)

ኢትዮጵያዊያን ለአንድ ሳምንት በዋሽንግተን ዲሲ ከትመው ሀገራቸውን፣ ባህላቸውን፣ ቀዬአችውን፣ ቤተሰባቸውን እያሰቡ በአንድነት በዓመታዊ ቀጠሯቸው የማይቀርበትን ፌስቲቫላቸውን አክብረዋል። በተመሳሳይ ሳምንት እና ቀናት ከሥስት ዓመታት በፊት ኢትዮጵያዊያን በጋራ የሚያከብሩትን ዓመታዊ የስፖርት እና ባህል ፌስቲቫል ESFNAን ለማፍረስ የተመሠረተው የከፋፋዮች ቡድን AESONE ዝግጅቱን በኮሎራዶ አሰናድቷል።

ይህ በጥቂት ገንዘብ አሳዳጅ ወረበሎች የሚመራ ቡድን ዓላማው እና ዒላማው የሼኽ መሐመድ አላሙዲን ሚሊዮን ብር ስለሆነ የሚፈልገውን ቅርጫ እስካደረገ ድረስ “ሕዝብ እና አንድነቱ ሲዖል ይግባ” የሚል ነው። አላሙዲ ዋናውን የስፖርት ፌዴሬሽን ESFNA ስፖንሰር ያደርጉ ስለነበር የእሳቸው ገንዘብ ሲቆም ፌድሬሽኑም ሕዝቡም በቀላሉ ይበተናል ተብሎ ታልሞ ነበር።
ሌላው ተያይዞ ያለው ዐቢይ ጉዳይ ደግሞ ህወሓት ዲያስፖራው ውስጥ ሰረስሮ ገብቶ በሀገር ቤት የፈጠረውን የአፋና ና ቁጥጥር መረብ በውጭ ሀገርም የማንሰራፋት ስሌት ነበር።

ሆኖም ይህ በክፋት እና በሴራ የተመሠረተ ቡድን AESONE ከዋናው ፌዴሬሽን ተሰንጥቆ በመውጣት አንድነትን ለመሰንጠቅ ያደረገው ጥረት ሊሳካ አልቻለም። ከዚያ ይልቅ ከፌዴሬሽኑ መርዝ ተነቀለለት ማለት ይቀላል። ይሁን እንጂ አሁንም በአንዳንድ የአላሙዲን ገንዘብ ናፋቂዎች በመጠቀም ሕዝብ ከሀገሩ ርቆ በአንድነት ህብር ሰርቶ ተደስቶ ቀጣዩን የሚናፍቅበትን የኢትዮጵያዊያን ስፖርት በሰሜን አሜሪካ ፌዴሬሽንን ለማፍረስ ጥረታቸውን ቀጥለዋል። በፌድሬሽኑ ያሉ ኢምንት ልዩነቶችን ወይም ስህተቶችን በማጉላት ውስጥ ለውስጥ ለመከፋፈል ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ተልዕኳቸውን ሊፈጽሙ ይፍጨረጨራሉ።

ነገር ግን ንቁው ማህበረሰብ ሴራውን በመገንዘቡ የተነቀለው መርዝ ላለፉት ሦስት ዓመታት ባዘጋጀው ተመሳሳይ ዝግጅት ላይ ለመታደም እግሩን አላነሳም። እባብ መኖሩን አውቆ ወዳለበት የሚሄድ ሞኝ የለምና። ሰው እንዴ ሊታለል ይችላል ሁልጊዜ ገን ከቶ አይታሰብም::
neway3
በAESONE ውድድር ላይ የሚሳተፉ ተጨዋቾች በብዛት የጊዮርጊስ ተጨዋች የነበሩ፣ በተለይም ከአብነት እና አላሙዲ የክለቡ ባለቤትነት ዘመን ተጫውተው ያሳለፉ ናቸው። በቀጥታ ሲጠየቁ ይሉኝታ ይዟቸው እና ፈርተው ይሄዳሉ። ከሪም፣ሙልዓለም ረጋሳ፣ አሸናፊ ሲሳይ፣ አዳነ ግርማ፣ የሙሉጌታ ከበደ ልጅ ሳይቀር በእነ አብነት ቡድን ተጠርተው ተሳትፈዋል። ፈርዶባቸው!

ይሄ ቡድን ከሼኹ ከ1 ሚሊዮን ዶላር በላይ እየወሰደ ዋሽንግተን ዲሲ ላይ ለሁለት ዓመታት በግዙፍ ስታዲየም ዝግጅት አዘጋጅቶ ከፋፋዮች እና ጥቂት የህወሓት ደጋፊዎች በተገኙበት ወና ሆኖ በአሳፋሪ ሁኔታ ተጠናቋል።

ይህ ክሽፈቱን በመረዳት ዘንድሮ ወደ ኮሎራዶ ግዛት ዴንቨር በመሄድ ከስታዲየም ወረድ ብሎ በትምህርት ቤት ሜዳ ሌላ ዕድሉን ሞክሯል። ወደ ዴንቨር ሲወሰድ ዋናው ቀመር በከተማዋ በረካታ የትግራይ ብሔር ተወላጆች በመኖራቸው ቢያንስ እነርሱ ገብተው በድኑን ቡድን ነፍስ ይዘሩበታል ተብሎ ነው።

አንድ በዝግጅቱ ላይ ከእንግዲህ በፍጹም እንደማይሄድ በምሬት የነገረኝ ተጨዋች “ዝግጅቱ የህወሓት ፌስቲቫል እንጂ የኢትዮጵያዊያን አልነበረም። እዛ በመሄዴ ለራሴ አፈርኩ” ብሎኛል። ገንዘብ ይሰጣችኋል ተብለው የሚሳተፉት ቡድኖች ወጣት ተጨዋቾች በቀን አስር ዶላር ብቻ እንዴት ይሰጠናል ብለው አኩርፈዋል። “አላሙዲ የሚለግሰው ገንዘብ በጥቂቶች እየተበላ እኛ ምን ቤት ነን? በዚያ ላይ ከሕዝባችን ተለይተን እስከመቼ” ብለዋል።

ከዋናው አንጋፋ ፌዴሬሽን ESFNA ተሰንጥቀው የተነቀሉት መርዞች ቡድኑን ሲመሠርቱ መፍጠር የፈለጉት ይህንኑ ነበር፣ መከፋፈል። ለሆዳቸው እስካደሩ ድረስ የማህበረሰብ እና የእሴቱን ዋጋ የሚያሰላስል ህሊና የላቸውም። ገንዘብ ፍቅር አይገዛም። የአላሙዲ እርድታ ቢቀር የሕዝቡን አብሮነት አልበተነውም። በተቃራኒው የጠላት ስሌት የገባው ሕዝብ በእልህ ዓመታዊውን ፌስቲቫል ማድመቅ ውዴታው ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነት ግዴታው አድርጎታል።

ተመሳሳይ ሴራዎች እና ሸፍጦች በቤተክርስትያን፣ በመስጊድ፣ በጓደኛሞች ማህበራት እና ፖለቲካ ድርጅቶች ውስጥ ይፈጸማሉ። ከድርጊቶቹ ጀርባ ያለው አውራ አቀናባሪ ደግሞ ህወሓት ነው።

በመሆኑም በማንኛውም ህብረት ውስጥ ላሉት ችግሮች ህጸጾችን ከማጉላት ይልቅ እልባት በመስጠት እና ልዩነቶችን ለማጥበብ በመስራት መተራረሙ ከመበታተን ያድናል።ስለዚህ ማህበርን፣ ማህበረሰብን፣ ብሔርን፣ ጎረቤትን፣ ቤተሰብን እና የራስን አዕምሮ በጥቃቅን ጥቅማ-ጥቅም የሚሸነሽነው የህወሓት ሥርዓት እንዲወድቅ ሁሉም ተቆርቋሪ ዜጋ የበኩሉን አስትዋጻዖ ማበርከት ግዴታው ነው።

↧

“ሊቀመንበራችን ትግል ሜዳ ውስጥ ነው”–የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ መግለጫ

$
0
0

Ginbot 7 Birhanu Nega
July 19, 2015
ሐምሌ 12 2007 ዓ.ም.
ህወሓት በኢትዮጵያዊያን እና በኢትዮጵያ ላይ ያሰፈነው ዘረኛና ፋሽስታዊ አገዛዝ እንዲያበቃ፤ በምትኩም ፍትህ፣ ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ የሰፈኑበት የፓለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት እንዲመሠረት እና የሀገራችን አንድነት በጠንካራ መሠረት ላይ ለማኖር አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ተገዶ የገባበት የመረረ የአመጽ ትግል መጀመሩን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያዊያን የነፃነት አርበኞች በጀግነትና በጽናት እየታገሉ ነው።

ይህ ትግል በባርነትና በነፃነት መካከል የሚደረግ ወሳኝ ትግል ነው። የዚህ ትግል ውጤት የእኛ የዚህ ዘመን ትውልድ ሕይወት ብቻ ሳይሆን የአገራችንን የወደፊት ታሪክ፤ የልጅ ልጆቻችንን ሕይወት ይወስናል። በዚህም ምክንያት ይህንን ትግል በድል መወጣት ግዴታችን ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ለነፃነት ግድ ያለው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከጎናችን ሊቆም ይገባል።
አርበኞች ግንቦት 7 አመራሩን ሁኔታዎች በፈቀዱ መጠን እና ትግሉ በሚጠይቀው ቦታ እንዲገኙ የሚያደርግ መሆኑ ሲገልጽ ቆይቷል። አሁን ትግሉ በደረሰበት ደረጃ የአመራሩ በትግሉ ሜዳ ውስጥ መገኘት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ሊቀመንበሩን ጨምሮ አመራሩን ወደ ትግሉ ሜዳ አንቀሳቅሷል። በዚህም መሠረት የንቅናቄው ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ ትግል ሜዳ ወርዷል።

ትግሉ መሯል። ወሳኝ የሆነ ትግል ውስጥ ገብተናል። የትግሉ መሪዎች የሕይወት መስዋዕትነት እሚከፈልበት ቦታ ይገኛሉ። በአሁኑ ሰዓት የንቅናቄው አመራር በተሟላ ሁኔታ በትግሉ ሜዳ ውስጥ እንዲገኝ ማድረግ ተችሏል። ኢትዮጵያዊያን እጅ ለእጅ ተያይዘን ዘረኛው የህወሓት አገዛዝን ከጫንቃችን ለማስወገድ ቆርጠን እንድንነሳ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።

ኢትዮጵያን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ የሚያወጣው አርበኞች ግንቦት 7 ብቻ አይደለም። ስለሆነም ከሌሎች ድርጅቶች ጋር የሚደረገው ትብብር ቀዳሚ ትኩረት ከተሰጣቸው ሥራዎች አንዱ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተቀጣጠለው ሕዝባዊ አመጽ ለድል እንዲበቃ ይታገላል። ኢትዮጵያዊያንም በያሉበትም በተመሳሳይ ልዩነቶቻቸውን አቻችለው በህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ ላይ ክንዳቸውን እንዲያነሱ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።

እነሆ የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በአካል ትግል ሜዳ ውስጥ ይገኛል። የሚችል ሁሉ እንዲከተል፤ መከተል የማይችል በያለበት ሁኖ ሁለገብ ትግሉን እንዲያጧጥፍ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ

↧

የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና ነአምን ዘለቀ አዳዲስ ፎቶዎች ከአስመራ (ይናገራል ፎቶ)

$
0
0

ትናንት ዘ-ሐበሻ በሰበር ዜና ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና ነአምን ዘለቀ አስመራ መግባታቸውን መዘገባችን ይታወሳል:: በዚህ መሰረት የነዚህ አመራሮች ፎቶ ግራፎች ከአስመራ ደርሰውናል::
ዶ/ር ብርሃኑ ኤርትራ በገባ በጥቂት ሰዓታት ልዩት የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ፖለቲካ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ክፍል ወደሚገኝበት ቦታ በማምራት ከህዝብ ግንኙነት ክፍሉ አርበኛ ታጋዮች ጋር ምሳ በልተዋል:: ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ለህዝብ ግንኙነት ክፍሉ አርበኛ ታጋዮች ባስተላለፉት መልዕክት
“ከሁሉም ነገር ዓላማ ያስተሳሰረው ስለሚልቅ፤ ለእኔ ለአገሩ ህይወቱን መሰዋዕት ለማድረግ ከተዘጋጀ ሰው የሚበልጥ ምንም ነገር በምድር ላይ ባለመኖሩ ወደ እናንተ መጥቻለሁ፡፡ የመጣሁትም እናንተን ለማስተማር ሳይሆን ከእናንተ ለመማር ነው… ለነፃነታችን አብረን እንሞታለን…” ብለዋል::
Birhanu Nega asmera

Birhanu nega asmera er

Birhanu nega photo

Birhanu Nega Bonger G7

G7 Birhanu nega

↧

ተግባር ትጥቁ ተግባር –ተግባር ስንቁ ተግባር –ተግባር ትንፋሹ –ተግባር ነው! (ሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 19.07.2015 /ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ/

„የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል እግዚአብሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል“ / ምሳሌ 16 ቁጥር 9/

Birhanu nega photoየተግባር ግብ ተግባር ነው! ተግባር ስርክራኪ የለውም። የተግባር አሰር የለውም። ተግባር አቮል ነው። ተግባር በኽር ነው። ተግባር ዓይነታ ነው። ተግባር የነጠረ ንጡህና ፃድቅና ፀዲቅም ነው። ንጡህና ጻድቅ ደግሞ ልክስክስ የሆኑ ጉድፎች ክፍሉ አይደሉም – አይሆንም። ስለሆነም ተግባር፣ ተግባርን ጸንሶ ተግባርን ይገላገላል እንጂ ተግባር ክፋትን – ቂም በቀልን ጸንሶ ዬእንግዲህ ልጅን – አይገላገልም።

የተግባር ሩኹ ብሩኽ – ራዕይ ነው። ብሩኽ ራዕዩን ለማግኘት በሠርግና ምላሽ አለመሆኑን ጠንቅቆ – ይገነዘባል። ተግባር መከራን ለመቀበል፤ ፍዳን – ለመሸከም፤ አሳርን ለማስተናገድ የተዘጋጀን ጀግና – ይደግፋል፤ ይመራል – ያስተዳድራል። የተግባር ድፍረቱ የሚመነጨው ከተነሳበት እውነተኛ ህዝባዊ ዓላማና ካስገኘው ውጤት – ይነሳል። አመሻሽ ላይ ተነስቶ እንቅልፍ እንቅልፍ ይለው የነበረውን እንጉልች አውሎ ቁጭ በል ያሰኘው እርምጃ እንሆ — ተግባርን ስንቅና ትጥቅ ያደረገው ትንፋሽ አስቀድሞ፤ በተግባር አዝማችነት ተስፋን ለማማፋፋት ከተግባር ተነስቶ – ተግባር ላይ ሰከነ። ተመስገን!

አዎን! የተግባር መነሻው ተግባር ነው። የተግባር መድረሻው ተግባር ነው። ተግባር ሁልጊዜም አሸናፊ ነው። ተግባር ሁልጊዜም ድል ላይ ነው። ተግባር እንኳንስ እሱ ሊሸነፍ ተሸናፊዎችን ሳይቀር በነጠረ ጭብጥ በመሆኑ – ነፃ ያወጣቸዋል። የተግባር መሳሪያው ተግባር ብቻ ነው። የተግባር ጠበቃው ተግባር ብቻ ነው። የተግባር መከላከያው ተግባር ብቻ ነው። ዳኛው ተግባር መከረኛውን አሁንም በተግባሩ – ይክሰዋል። በጥርስ የተያዘው ሌት ተቀን የሚከተከተውን፣ ደመ -መራሩን – መከራውን እንደ ጌጥ ቆጥሮ ቀልጦ ሻማ እንዲሆን – ይረዳዋል። የተግባር ታቦቱ  -ድርጊተኛው ነው። የተግባር ሽልማቱ የተሰጠው መክሊቱ ነው።

አሁንስ? እኮ አሁንስ? ምን ይባል ይሆን። ክርችም ዝግት ይሆን – ይሆን? ፀጥ ረጭ ይሆን? ወና ይሆን ዕጣ ፈንታው የአታሞው፤ ወይንስ ደግሞ ያው እንደተለመደው የለወጥ ንፋስን እንዘውር ተብሎ አካኪ ዘራፍ ይባል ይሆን?  ዬዕንባ ወታደር አይተኛም – አያንቀላፋም። ይልቁንም ዕንባን የረገጠውን በተግባር አብነት በማስተማር፤ በማደራጀት ቀንዲልነቱን በተግባሩ  – ያረጋግጣል።

ተስፋ ተግባር ነው ወታደሩ፤ ለተስፋ ድርጊት ነው – መጽናኛው፤ ለተስፋ መሆን – ሁነኛው። እነሆ ሁነ። እነሆ ተስፋ አዎ ሆነ። ተስፋ ነው ሆነ። ተስፋ በድርና ማግ ራዕይን ዕውን ለማድረግ የበዛውን መከራ ለመቀበል  – እውነትን ፈቀደ። ተመስገን!

ይህ ታሪካዊ ጉዞ ይህ አደራን የተቀበለ ጉዞ ዛሬን ለማሳደር ነገን አብቅሎ ያሰብል ዘንድ ትውልዳዊ ኃላፊነትን ወዶ በመቀበል የግዙፉ ትውፊት ተልዕኮ አስኳል ነው። ሞትን ፈቅዶ – ለተቀበለ፤ ሞትን ወዶ –  ላከበረ፤ ሞትን ናልኝ ብሎ ለመገናኘት ለገሰሰ ወገን ቅድስት ቤተክርስቲያናችን፤ እንዲሁም መስኪዶቻችን ማናቸውም ቤተ አምልኮች ሁሉ በዚህ ነፍሰጡር ሴቶች ተረግጠው ጽንስ ሞት በተፈረደበት ዘመን ያሉ ሁሉ ይህን ጊዜ የሱባኤ ወቅት በማድረግ ማህበረ ምዕመኑን ወደ አንድ የጸሎት አቅጣጫ በመምራት ሰፊ የሆነ የተደራጀ የጸሎት ተግባር በግልና በጋራ እንዲከወንብት በማደረጉ በኩል ሰፊውን ድርሻ በመውሰድ በይፋ ዕወጃ ከጎን መሰለፍ ያለባቸው – ይመስለኛል። አባቶቻችን ለድል የበቁት ባለ ሀገር፣ ባለ ሰንድቅ ዓላማ፣ ባለ ማንነት፤ በለ ዕምነት እንድንሆን ያደረጉን በዚህ መንገድ – ነው።

„በቃኝ“ እንዲህ ነው። „በቃኝ“ ለቁርጥ ቀን „የቁርጥ ልጅ ነው“ የአሻም ምላሹ „የአሻም ጉልላት“ ነው። የቁጭ በሉ ዳንኪራ አሁን አድራሻውን መፈለግ አለበት። የሚያዘናጉ ሆነ ትጥቅን የሚያስፈቱ ዘመቻዎች ሁሉ እዩኝ እዩኝ እንዳሉ ሁሉ ደብቁኝ ደብቁኝ ማለት – አለባቸው። አጀንዳቸው እነሆ እንዲህ – አከተም። ሊቀጠል፣ ሊሰፋ ወይንም ሊጣፍ የማይችል አጀንዳ ግብዕቱን የሚፈጸመው እንዲህ በተግባር አሸናፊነት ነው። አዎን ተግባር ሻንፕዮን ነው። የተግባር መዳሊያው መሆን ብቻ ነው። ሆኖ መገኘት!

ያመነ – የተቀበለ – የቆረጠ – ለድል ይበቃል። ድሉ የዕንባ ነው። ድሉ የህዝብ ነው፤ ድሉ የነገ ነው። ድሉ የትውልድ ነው። ድሉ የተስፋ ነው። ድሉ – ለተገፉት ነው። ድሉ ለመከረኞች ነው። ድሉ የኢትዮጵያ ነው። እርግጥ ነው ድሉ ለቀለጤዎችና ለድሎተኞች ግን አይሆንም፤ እንዲያውም ዛሬ ትቅማጥ በትቅማጥ እንደሚሆኑ – አስባለሁ።

ቅድስት እናቴ እመቤቴ፤  የሰማይና የምድር ንግሥት፤ የሰማይና የምድር እምቤት፤ የሰማይና የምድር ልዕለት እናት ናትና፤ ሩህሩህ ናትና፤ ስደቱንም ታውቀዋለችና መክሊትን ጠብቂ። ጥላ ከላላ ትሁናችሁ። እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

የዕለቱ ዕርእሰ አንቀጽ ምንጭ – http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45166

 

አርበኞቻችን መርሆቻችን – አርበኞቻችን መንገዶቻችን ናቸው!

ቅዱስ ጊዮርጊስ አደራህን – ተጋድሎውን ባርክ!

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

↧
↧

ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ኤርትራ እንደገባው ሁሉ በቅርቡ አራት ኪሎ ቤተመንግስት ይገባል!!!

≫ Next: Hiber Radio: የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ኤርትራ ትግሉን በአካል መቀላቀል ሰፊ መነቃቃት መፍጠሩና የአገዛዙ ደጋፊዎች ድንጋጤ፣ በዶ/ሩ ጉዞ የጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ትንታኔ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሁለት መኪናዎች ውስጥ የተደበቁ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር መዋል፣መድረክ ፕ/ት ኦባማ በጉብኝታቸው ወቅት እንዲያናግሩት ጥያቄ ማቅረቡ፣የአቶ አንዳርጋቸው ፍርድ ቤት መቅረብ አጠራጣሪነት፣ አንድ ወታደር ሶስት ኮሌኔሎችን ገድሎ በርካቶችን አቁስሎ ራሱን ማጥፋቱ ፣ ካናዳ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ዜጋዋን ችላ ማለቷ ማስወቀሱ፣ ገንዘቤ ዲባባ የእህቷን ሪኮርድ ለመስበር ፍላጎቷን መግለጿ፣ የዑበር የ7.3 ሚሊዮን ዶላር መቀጣትና ሌሎችም
$
0
0

ሳሙኤል አሊ ከኖርዌይ

የወያኔወች የውስጥ ጅማታቸው መፈታት ከጀመረ ሰነባብቷል። የሚይዙትና የሚጨብጡትን ካጡ ትንሽ ቆየት ብለዋል በወያኔ ሃሳብ በዘር ፖለቲካ እየጠላለፈ ምስራቁን ከምዕራብ፤ ደቡብን ከሰሜን፤ እያነሳሱ  የራሳቸውን ወታደሮች አጠናክረው ሰለ አገሩ ቀና አሳቢውን ወይም መብቴን እጠይቃለው የሚለውን እየገደሉ አገሩን በሙሉ በራሳቸው ቁጥጥር ስር አድርገው መቶ አመት እንገዛለን በሚል እቅድ ተነሳስተው ኢትዮጵያዊኑ እርስ በእርስ እንዲጠላላና እንደጠላት እንዲተያዩ እያደረጉት ነው ።  በከፍተኛነት የባንዳነትን ስራ እየሰሩ እራሳቸውን በሁሉም እረገድ የበላይ አድርገው ሌላውን ዜጋ እንደሁለተኛ  ወይም እንደ ባርያ ለመግዛት ቀን ከለሊት እየሰሩ ያሉት የወያኔ  ቡድን የደም ዝውውራቸው የሚቋረጥበት የልቦና ተንኮላቸው የሚኮላሽበት የዘር መረባቸው የሚበጣጠስበት ትግል ተጀምራል። ያርበኞች ግንቦት ሰባት የነጻነት ጥሪ ወደ ትጥቅ ትግል መግባት ሲያስጨንቀው ከርሞ  ዛሬ ጭቆናው ይብቃ ያለው  ሕዝቤ  የባርነት ኑሮን  አልቀበልም ያለው ኢትዮጵያዊ በግፈኛው ወያኔ ላይ መሳርያውን አንስቶ ወደ ግንባር በመትመም  ጀግንነቱን እያሳየ ይገኛል። አርበኞች ግንቦት ሰባት በይፋ ጦርነቱን መጀመሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ በጉጉት የሚጠብቀው የነበረ ቢሆንም ወያኔወች ደግሞ  በጽኑ የሚፈሩት ጉዳይ ነበር። እንግዲህ የማይቀርላቸውን የጥፋት ዘመናቸውን ማቅረቢያውም በአርበኞች ግንቦት ሰባት በኢትዮጵያ የነጻነት ጥሪ በይፋ ተነግሮ ወያኔወችን በቆፈሩት ጉድጋድ በያሉበት ሊቀብር ተነስታል።

Birhanu Nega Bonger G7የግቦት ሰባት ሊቀመንበር ዶክተር ብርሃኑ ነጋ በሕዝብ ለማስጠላት ያልፈነቀሉት ድንጋይ  ያልማሱትም ጉድጓድ የለም። ስሚ አጡ እንጂ በአንዳንድ በውጪ በሚኖሩ ኢትዮጵያን ላይ ትንሽ ጉንጉምታ የሚፈጥር አዝማምያ  የነበረ ቢመስልም ዛሬ ግን ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ያንን ጉምጉምታ አጥፍተውታል። በርገር እየበሉ ጦርነት የለም፧ አሜሪካና አውሮፓ ቁጭ በለው አገር ቤት ያለውን ሕዝብ  ማስጨረስ የለም ፧ የሚለውን የወያኔ የማደናገርያ  የሃሰት ቅስቀሳ  የአርበኞች ግንቦት ሰባት  ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ከአውሮፓና ከአሜሪካ  ወደበርሃ  በመውረድ የአርበኞች ግንቦት ሰባትን ጦር መቀላቀላቸው ለሁሉም  ግልጽ ያደረገና ሁሉም ኢትዮጵያዊ ወያኔ የተባለውን ጭራቅ ለማጥፋት ቆርጦ  የተነሳ መሆኑን ያስገነዝበናል።  በኢትዮጵያ  አገራችን ሊደራደሩ ፍቃደኛ የማይሆኑ አገር ወዳድ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ ዶክተር ብርሃኑ ወደ ወረደው በርሃ  ወርዶ ወያኔን ዶግ አመድ  አድርጎ  ነጻነቱን እንደሚያውጅ የታወቀ ነው። ለዚህም ነው የአርበኞች ግንቦት ሰባት ከፍተኛ  አመራሮች  እንደ አንዳርጋቸው ጽጌ ለኢትዮጵያ ነጻነት በመታገል መስዋትነትን የከፈሉት።  ዛሬ እነ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ኤርትራ በርሃ  ገብተው መሰራት ያለበትን ስራ  እየሰሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ የብርሃኑን ጮራ የሚያይበትን ለወያኔ ደግሞ  ከኢትዮጵያ ምድር የሚጠፋበትን መንገድ ቀይሰው  በርሃ በመውረድ ታላቋን አገር ከጥፋት ለመታደግ መሰዋትነት እየከፈሉ ያሉት።

ዛሬ ወያኔና የወያኔ አጫፋሪ ሁሉ ዶክተር ብርሃኑ ኤርትራ በርሃ ገባ ብለው ሲያሽማጥጡ የነበሩ ሁሉ ነገ አዲስ አበባ  ቤተመንግስት ገብቶ የኢትዮጵያን ሕዝብ የስልጣን ባለቤት ሲያደርግ ታዪታላቹ ፧ የነጻነት መዝሙር የሰላም ባንዲራውን ይዞ የኢትዮጵያን ሕዝብ በህብረት ሲያዘምር ታዪታላቹ። እመኑኝ ደርግ እንደወደቀው ወያኔም ይወድቃል፦ እንዳለው ሃብታሙ አያሌው; ዛሬም እመኑኝ ነገ ወያኔወች የዘረፋትን ሳይበሏት  ጎሮሮአቸው ላይ እንዳደረጉት  የኢትዮጵያ ሕዝብ ጉሮሮአቸው ላይ ይቆማል፧ እመኑኝ ኢትዮጵያን አጠፋለው ብሎ  የተነሳው ወያኔ  የኢትዮጵያ ሕዝብ  ያጠፋዋል፧ እመኑኝ ነጻነቱን ነፍገን፤ ጨቁነንና፤ እረግጠን፤ የበላይ ሆነን እኖራለን የሚለውን ወያኔ በሕዝባችን የጠነከረ ብትር ቀምሶ ከኢትዮጵያ  ምድር ይጠፋል፧  ይህ ቀን እሩቅ አይደለም ሁላችንም አርበኞች ግንቦት ሰባትን በመቀላቀል በመደገፍ ወያኔን ከኢትዮጵያ ምድር መውጫና  መግቢያ  አሳጥተን የምናጠፋበት ጊዜ  ቅርብ ነው።

ወያኔወች የማወናበጂያ  ዘዲያቸው በሙሉ ከሽፎባቸዋል  የወያኔን ክፋት ሁሉም ኢትዮጵያዊ አውቆታል አሁን ወያኔ የማጥፋቱን ስራ ብቻ ሳይሆን አገርንም የማዳኑ ስራ እየተሰራ ነውና፦  ሁሉም ኢትዮጵያዊ አገሩን ከጥፋት ለመታደግ ባአገር በነጻነት ለመኖር ለኢትዮጵያ አገርህ ስትል ተነሳ ድላችን በአገራችን ፤ መኖርያችን በአገራችን፤ መደሰታችን በአገራችን፤ ሆኖ ስደትና ችግር እንዲቆም ዛሬ የኢትዮጵያ ልጆች የወያኔ  የክፋት መረብ ከአርበኞች ጎን በመሰለፍ የድላችንን ዜና አብረን እናብስር።

ድል ለኢትዮጵያ  ሕዝብ

ሳሙኤል አሊ ከኖርዌይ

Email samilost89@yahoo.com

20.7.2015

↧

Hiber Radio: የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ኤርትራ ትግሉን በአካል መቀላቀል ሰፊ መነቃቃት መፍጠሩና የአገዛዙ ደጋፊዎች ድንጋጤ፣ በዶ/ሩ ጉዞ የጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ትንታኔ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሁለት መኪናዎች ውስጥ የተደበቁ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር መዋል፣መድረክ ፕ/ት ኦባማ በጉብኝታቸው ወቅት እንዲያናግሩት ጥያቄ ማቅረቡ፣የአቶ አንዳርጋቸው ፍርድ ቤት መቅረብ አጠራጣሪነት፣ አንድ ወታደር ሶስት ኮሌኔሎችን ገድሎ በርካቶችን አቁስሎ ራሱን ማጥፋቱ ፣ ካናዳ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ዜጋዋን ችላ ማለቷ ማስወቀሱ፣ ገንዘቤ ዲባባ የእህቷን ሪኮርድ ለመስበር ፍላጎቷን መግለጿ፣ የዑበር የ7.3 ሚሊዮን ዶላር መቀጣትና ሌሎችም

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ ሐምሌ 12 ቀን 2007 ፕሮግራም

<...>

ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ለህብር ሬዲዮ የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በረሃ መውረድ በትግሉ ላይ የሚያመጣውን ለውጥ በተመለከተ ተጠይቆ ከሰጠን ሰፋ ያለ ማብራሪያ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

<... ...> የጥሬ ስጋ አመጋገብ ባህላችን እና ኣለም አቀፍ የዘገባ ትኩረት ማግኘቱ( ልዩ ጥንቅር)

<...>

ዶ/ር መረራ ጉዲና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስለተባረሩበት ውሳኔ፣በአገር ቤት ስላለው የተቃውሞ ፖለቲካና የኦባማን ጉዞ አስመልክቶ ከሰጡን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

* የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ኤርትራ ትግሉን በአካል ለመቀላቀል መሔድ በማህበራዊ ሚዲያው ሰፊ መነቃቃትን ፈጠረ

– የአገዛዙ ደጋፊዎች ድንጋጤ ተስተውሏል

* አንድ ወታደር ሶስት ኮሌኔሎችን ገድሎ በርካቶችን ካቆሰለ በኋላ ራሱን ማጥፋቱ ተገለፀ

* በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሁለት መኪናዎች ውስጥ የተደበቁ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

_ አሽከረካሪዎቹ እየታደኑ ናቸው ተብሏል

* አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ለምስክርነት ፍ/ቤት እንዲቀርቡ የሰጠው ውሳኔ ተግባራዊነት አጠራጣሪ ሆኗል

* መድረክ ፕሬዝዳንት ኦባማ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ወቅት እንዲያነጋግሩት ጥያቄ ማቅረቡን ዶ/ር መረራ ጉዲና ገለፁ

– የአሜሪካ ኤምባሲ ባለስልጣናት በጉዳዩ ላይ ለመወያየት ቀጠሮ ይዘዋል

* ሁበር በካሊፎርኒያ የ7.3 ሚሊዮን ዶላር ቅጣትና በአንድ ወር ውስጥ አገልግሎቱን እንዲያቋርጥ ዳኛ ውሳኔ ሰጠ

– ውሳኔውን በመቃወም ኩባንያው ይግባኝ የማለት እቅድ እንዳለው ገለፀ

* የካናዳ መንግስት በኢዮጵያ ውስጥ የታሰረ ዘጋዋን ባለመወሰዷ ከፈተኛ ትችት ገጠማት

* ኬንያ ኢትዮጵያዊያን መኮነኖችንን ማሰሯን እና ለኪሳራ እንደዳረጓት ባለሰላጣናቱዋ ገለጹ

* የእስራኤል መንግስት ኢትዮጵያዊው አባ ወራን ከቤተሰቦቻቸው ነጥሎ ለያባርራቸው ወሰነ

* አምባሳደር ግርማ ብሩ መገንጠልን ከሚቃወሙ ወገኖች የከረረ ጥያቄ ገጠማቸው

– “እረ ሰለኮንደሚኒየም ከማወራት በፊት ኣንድ አድረጉን ፣አትገነጣጥሉን” አንድ ተቃዋሚ ለአቶ ግርማ ያቀረቡት ምክር

* አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ለ23 አመታት ያልተደፈረ የአለም ክብረወስንን ሰበረች

– የታላቅ እህቷን ረኮርድም ለመሰበር ቋምጣለች

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

↧

  የቀድሞ የምዕራብ አፍሪካዋ ቻድ አምባገነን ሂስኒ ሀብሬ በእስር ዋለ

≪ Previous: Hiber Radio: የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ኤርትራ ትግሉን በአካል መቀላቀል ሰፊ መነቃቃት መፍጠሩና የአገዛዙ ደጋፊዎች ድንጋጤ፣ በዶ/ሩ ጉዞ የጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ትንታኔ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሁለት መኪናዎች ውስጥ የተደበቁ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር መዋል፣መድረክ ፕ/ት ኦባማ በጉብኝታቸው ወቅት እንዲያናግሩት ጥያቄ ማቅረቡ፣የአቶ አንዳርጋቸው ፍርድ ቤት መቅረብ አጠራጣሪነት፣ አንድ ወታደር ሶስት ኮሌኔሎችን ገድሎ በርካቶችን አቁስሎ ራሱን ማጥፋቱ ፣ ካናዳ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ዜጋዋን ችላ ማለቷ ማስወቀሱ፣ ገንዘቤ ዲባባ የእህቷን ሪኮርድ ለመስበር ፍላጎቷን መግለጿ፣ የዑበር የ7.3 ሚሊዮን ዶላር መቀጣትና ሌሎችም
$
0
0

 

newsየቀድሞ የምዕራብ አፍሪካዋ ቻድ መሪ የነበረውና “የአፍሪው ፒኖቼ” ተብሎ ይታወቅ የነበረው ጨካኙ ሂስኒ ሀብሬ ለፍርድ እንዲቀርብ በሴኒጋል መንግስት ተያዘ።ፒኖቼ እንደ ሃብሬ በቺሌ ደቡብ አማሪካ ሰላማዊ ህዝብ በመጨፍጨፍ ይታወቅ የነበረ ነው።

ሂስኒ ሀብሬ በመፈንቅለ መንግስት ከተወገደ ጀምሮ ለሃያ ሁለት ዓመታት በሴኒጋል በጥገኝነት ኖርዋል። ሂስኒ ሀብሬ የተከሰሰው በኢሰብአዊ ድርጊት መፈጻምና ሰቆቃ ነው። የቀድሞው አምባገነን ፍርዱን እየጠበቀ ነው።ሀብሬ እአአ 1990 መፈንቅለ መንግስት ከስልጣን መውረዱ ይታወሳል።

ሁማን ራይትስ ዋች የተባለው የሰብአዊ መብት ጥበቃ ድርጅት ሂስኒ ሀብሬን ለአርባ ሺህ ሰዎች ሞት አላፊ ያደርገዋል።በስልጣን የቆየው ክ1982-1990 እአአ ነው።ከስልጣን ያስወገደው የዛሬው ቻድ ፕሬዚዳንት ኢድሪስ ዳቢ ኢትኖ  የሀብሬ መያዝ አንድ እርምጃ ወደ ፊት ነው “ከክፋትና ከአባገነንነት ነጻ የወጣች አፍሪካ” ሲል ተናግሯል። ሂስኒ ሀብሬ ክሱን ክዷል።

ይህን ያህል ዓመታት የሴኔጋል መንግስት የሂስኒ ሀብሬ ፍድ መቅረብ ሳይፈቅድ ቆይቷል።በሴኔጋል ፍርድ ቤት ሀብሬ መቅረቡ አዲስ ምዕራፍ ከፋች ይሆናል። እስተዛሬ የአፍሪካ አምባ ገነኖች በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ብቻ ነው ሲቀርቡ የነበሩት።ባለፈው ዓመት የተባበሩት መንግስታት ፍርድ ቤት (UN’s International Court of Justice) የሴኔጋል መንግስት ሀብሬን ለፍርድ እንዲያቀርበው አዝዞ ነበር። የየሴኔጋል መንግስትና የአፍሪካ አንድነት ሂስኒ ሃብሬ ለፍርድ መቅረቡ ላይ ስምምነት ተፈራርመው ነበር።

ሂስኒ ሃብሬ በቤጂየም ፍርድ ቤት ይፈለጋል በማለት አል ጃዚራ አትቷል። የቤልጂግ ዜግነት ያላቸው ቻዳውያ በቀረቡት ኢሰብዓዊ ወንጀል ተፈጽሞብናል በማለት።

↧

የእርዳታ ጥሪ…!

$
0
0

unnamedኣቶ ታደሰ ኣብራሃ የዓረና-መድርክ ኣባል ምርጫ 2007 ዓ/ም ተከትሎ በ 3 ሰዎች በሑመራ ማይካድራ ቀበሌ መገደላቸው ይታወቃል።

ኣቶ ታደሰ ኣብራሃ የሁለት ህፃናት ኣባት ሲሆኑ የ70 ዓመት ሽማግሌ ወላጅ እናታቸውም ጡዋሪ ነበሩ።

ኣቶ ታደሰ ኣብራሃ ሲገደሉ ወይዘሮ ኣኸዛ ፃዲቅ የ70 ሽማግሌ፣ ህፃን ሚኪኤለ ኣብራሃ የ 15 ዓመት ልጅና ሚልዮን ታደሰ የ 7 ዓመት ህፃን ያለ ጧሪና ያለ ኣሳዳጊ ቀርተዋል።

ኣቶ ታደሰ ኣብራሃ በኣገራቸው በሰለማዊ መንገድ ሲታገሉ የተሰዉ ጀግና ከመሆናቸውና እነዚህ ህፃናት ልጆቻቸው ወደ ጎዳና ተበትነው ለኣደጋ ሳይጋለጡ ሁላችን ኢትዮዽያውያን የተቻላችን ድጋፍ እንድናደርግላቸው ዜግነታዊ ሃላፍነታችን እንድንወጣ ግድ ይለናል።

ስለዚህ የምንችለው ድጋፍ በኣያታቸውና ሞግዚታቸው ወይዘሮ ኣኸዛ ፃድቅ ገብረሚካኤል የተከፈተላቸው የባንክ ሂሳብ ቁጥር Z57508001815 የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ሒዋነ ቅርንጫፍ እንድታስገቡላቸው በት ህትና እንጠየቃለን።

ሃምሳ ሎሚ ለኣንድ ሰው ሸክሙ ለሃምሳ ሰው ጣእሙ ነውና እጃችን እንዘርጋላቸው።

↧
↧

የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ጉዞ…ከክንፉ አሰፋ(ጋዜጠኛ)

$
0
0

“…ከዚህ በኋላ ህዝብ ሰብስቦ ማውራት ላቆም ነው። ጊዜው ተቀይሯል። ትግል ለደካማ መንፈስ አይሆንም። ትግል መውደቅን ይጠይቃል። ሲወድቁ ግን ለመነሳት መሞከርን ይጠይቃል። ስንወድቅ ልታዩን ትችላላችሁ ስንነሳ ግን ታዩናላችሁ … ” ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ይህንን የተናገሩት የአስመራ ጉዟቸው ከመሰማቱ ጥቂት ቀናት በፊት ነበር። ንግግሩ ለብዙዎች ግርታ መፍጠሩ አልቀረም። ከቀናት በኋላ የኤርትራን ምድር ሲረግጡ “ስንነሳ ግን ታዩናላችሁ…” ማለታቸው ግልጽ ሆነ።
ከምርጫ 97 በፊት ዶ/ር ብርሃኑ በፖለቲካ ስብእናቸው የሚታወቁት ለሰላማዊ ትግል ባላቸው የከረረ አቋም ነበር። በእስር ቤት ሆነው በጻፉት “የነጻነት ጎሕ ሲቀድ፤ …” መጽሐፋቸው ሰላማዊ ትግል ያለውን የሞራል፣ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ የበላይነት ምሳሌ እያስቀመጡ ዘርዝረዋል።
ለዚህም ነበር ከሰላማዊ ትግል ወጥተው “ሁለገብ ትግል” ለማካሄድ ማቀዳቸውን ሲገልጹ ለብዙዎች ድንገተኛ እና አስደንጋጭ የሆነው። የጦርነትን አስከፊ ገጽታ ሲነግሩን የነበሩ እኝህ ምሁር በአንድ ግዜ ወደ ተቃራኒው የትግል ስልት ሲዞሩ ያቀርቡት የነበረው ምክንያት በወቅቱ ብዙዎችን ሊያሳምን አልቻለም። ምክንያቱም አመጽ ወይንም ጦርነት ከባድ ነገር ነው። ገንዘብ እና ግዜን ይበላል። ከሁሉም በላይ የህይወት መስዋእነትን ይጠይቃል። የሰላማዊ ትግሉ ስልቶች ገና በደንብ አልተፈተሹም የሚሉም ጥቂቶች አልነበሩም።

Birhanu nega asmera er
ከአምስት ግዜ ምርጫ በኋላም ህወሃት ሕዝብ ላይ መቀለዱን አላቆመም። በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉትንም ጭራሽ ወደ ጫካ እንዲገቡ፣ አልያም እንዲሰደዱ አማራጭ መስጠት ያዙ። የትጥቁን መንገድ “ጨርቅ ያርግላችሁ” ሲሉም አሾፉ።
የ “ምርጫ 2007″ ውጤት በተሰማ ማዕግስት ከዴንቨር-ኰሎራዶ አንድ የቀድሞ ህወሃት ታጋይ ስልኬ ላይ ደውሎ እንዲህ አለኝ። “ግዜው የኛ ነው። ገና መቶ አመት እንገዛችኋለን። ታዲያ ስንገዘችሁ ዝም ብለን አይደለም። እየረገጥን እንገዛችኋለን…” ሰውየው እኔ እንድናገር እንኳን እድል አልሰጠኝም። ስለምርጫው ውጤት በድረ-ገጾች ላይ የሰጠሁት አስተያየት እንዳበሳጨው ገባኝ። በትግርኛ እና በአማርኛ እያቀላቀለ ተሳደበ። ዘር እና ሃይማኖትን ጭምር እየጠራ ተሳደበ። በትእቢት የተወጠረው ይህ ሰው ሙሉ ስሙን እና አድራሻውን ሳይቀር ይናገር ነበር። “ከፈለግክ ቅዳኝ። ማንንም አንፈራም!” ይል ነበር። እርግጥም ድምጹ በቴሌፎኔ መቅጃ ሳጥን ውስጥ ቀርቷል። ይህንን አጸያፊ ስድብ መልቀቁ ወገን ከወገን ማጋደል ይሆናል በሚል እሳቤም ለግዜው ይዤዋለሁ።
ማንነትን የሚፈታተን፣ ክብርን የሚነካ ንግግር ነው። ስድቡን ሁሉ በትእግስት ከሰማሁ በኋላ አንድ ቃል ብቻ ተናግሬ ስልኩን ዘጋሁት። “ትዕቢት ውድቀትን ትቀድማለች።”
የያዝኩትን ትንሽ መረጃ በመንተራስ ስለሰውየው ማንነት አንዳንድ ነገር ማወቅ ቻልኩ። ሰባት አመት የህወሃት ትግል ውስጥ የነበረ ሰው ነው። ይህ ግለሰብ ዴንቨር ኮሎራዶ ከአመታት በፊት ሲገባ ባዶ እጁን ነበር። አሁን ግን ሚሊየነር ሆኗል። የህወሃትን የተዘረፈ ገንዘብ በዶላር ለማጽዳት ወደ ዴንቨር የሚላኩ ሰዎች ቀጥር ቀላል አይደለም። እየረገጥን ገዝተን፣ እየረገጥን እንዘርፋለን፣ ይህንንም አሜን ብላችሁ ተቀበሉ ነው የሚሉን። ከባዶ ተነስተው መጠን የሌለው ስልጣን እና ገንዘብ ሲያካብቱ፤ በያዙት ነገር ይታወራሉ። ድንቁርና ሲታከልበት ደግሞ ስልጣናቸው ዘለአለማዊ፣ ሃብታቸውም የማያልቅ ይመስላቸዋል።
እንደዚህ አይነቶች ወንድነትን እና የሃገርን ክብር የሚፈታተኑ ነገሮች ተቆጥረው አያልቁም። ተሳፋሪዎችን ይዞ እየበረረ ያለ የአየር መንገድ አውሮፕላን በአንድ ካድሬ ትዕዛዝ እንዲመለስ የሚደረግባት ሃገር ሆናለች ኢትዮጵያ። ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ያገኘሁት አንድ መረጃ የሚያሳየን ይህንኑ ነው። ከአዲስ አበባ ናይሮቢ-ኬንያ ይጓዝ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራውን ከጀመረ በኋላ እንዲመለስ መደረጉ እና በዚህም ምክንያት አየር መንገዱ የሁለት መቶ ሺህ ዶላር ኪሳራ ደርሶበታል። ይህ የሆነው ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ አውሮፕላኑ ውስጥ ስለነበር ብቻ ነው። እነዚህ ሰዎች ሃገሪጥዋን የግል ንብረታቸው አድርገዋታል።
በፈለጉ ግዜ፣ የፈለጉትን ያስራሉ። በፈለጉ ግዜ የፈለጉትን ይለቅቃሉ። በእስር ላይ ከሉ 19 ጋዜጠኞች ይልቅ ለአንድ ባእድ መሪ ክብር የሚሰጡ፣ በአልሻባብ ከሚገደልው ሰራዊት ይልቅ ለአሜሪካ ብሄራው ጥቅም የሚጨነቁ የውስጥ ባዕዳን ናቸው ስልጣኑን በሃይል ያየዙት።
20 አመታት በአንድ ርእዮተ-ዓለም፣ በአንድ አገዛዝ፣ በአንድ ሰው አስተሳሰብ መዝለቅ እጅግ እጅግ ይከብዳል። በተለይ ደግሞ በምእራቡ አለም ውስጥ ለሚኖር ሰው ፍጹም የማይታሰብ ነገር ነው። በ97ቱ ግድያ እጅግ ተቆጥቶ የነበረው ሰር ቦብ ጌልዶፍ “መቼ ነው የምታድጉት? እስቲ እደጉ!” ብሏቸው ነበር። አሁንም አላደጉም። አሁንም ሰው እየገደሉ ነው። ለማደግ የምኒሊክ ቤተ-መንግስት ሃያ አመታት መቆየት አያስፈልግም። ለእድገት ለውጥ ያስፈልጋል። የስርዓት ለውጥ፣ የሰው ለውጥ፣ የአስተዳደር ለውጥ፣ የአቅጣጫ ለውጥ፣ የአስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልጋል።
በርካቶች በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ለማምጣት እጅግ ጣሩ። ጥረታቸው ግን እንደ ደካማነት ተቆጠረባቸው። በያዙት የጦር መሳርያ ብቻ የሚተማመኑ ጉልበተኞች ቀለዱባቸው። የህዝብን ድምጽ እየሰረቁ መቀመጣቸው ሳያንስ መራጩን ሕዝብ እያሳደዱ መበቀል ያዙ። ኢትዮጵያ በሰላማዊ ትግል ለውጥ ማምጣት ምርጫ ለአምስተኛ ግዜ ተሞከረ። አምስቱም ተጭበረበረ። ከአሁን በኋላ በምርጫ ለውጥ እናመጣለን ብሎ ማሰብ የማይቻልበት ደረጃ ላይ እንደሆነ የምርጫ 2007ቱ ትዕይንትን ብቻ ማጤኑ ይበቃል። በታሪክ 100% አሸነፍኩ ብሎ የተናገረ አንባገነን መንግስት በኛው ምድር ተፈጠረ። ይህ ሕዝብ ላይ ማፌዝ ነው። ትዕቢት፣ ድፍረት እና ንቀት የተሞላበት ፌዝ። “ምንም አታመጣም!” አይነት ንቀት!
በፖለቲካ አግባብ ጦርነት የዲፕሎማሲ ጣርያ፣ የሰላማዊ ትግል መጨረሻው አማራጭ ነው።
ከዚህ የአገዛዝ ንቀት በኋላ ህዝብ ለአመጽ ቢነሳ ተጠያቂው ያለህዝብ ይሁንታ ስልጣን ላይ ያለው ስርዓት ብቻ ነው። ህዝቡን ወደ ስደት እና ወደማይፈልገው አመጽ እየመሩት ያሉት እነዚያው የስልጣን እና የንዋይ ጥመኞች ናቸው። ይህ ንቀት ከትጥቅ ትግል ጋር ችግር አለብኝ የምንል ወገኖችን እንኳን የሚፈታተን ነገር ነው።
ዶ/ር ብርሃኑ ሲተቹበት የነበረው ሌላው ጉዳይ ደግሞ ትግሉን ከርቀት መምራት ያለመቻሉ ነገር ነበር። በሻእቢያ ላይ ያለው ጥርጣሬ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ይህ ጉዞ በዶ/ር ብርሃኑ ላይ ይነሳ የነበረውን የሞራል እና የሃላፊነት ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል። ለሰራዊቱ የመተማመን፣ ለህዝቡም የመነሳሳት ስሜት ይፈጥራል።
ከ21 ዓመት በላይ ያለ ለውጥ መቀመት በጣም ያሰለቻል። 21 አመት እየረገጡ እና እየዘረፉ መቀመጥ ይበዛል። ኢትዮጵያ ለውጥ ያስፈልጋታል። የኢትዮጵያ ህዝብ ፍትሃዊ ስርዓት ያስፈልገዋል። በሰላማዊው መንገድ ለለውጥ የተሰለፉ ሃይሎች እየታፈኑ፤ እየተሰቃዩ፣ እየተገደሉም ነው። እየተገደሉ የሚገድሉ ሲነሱ “ባንደግፋቸውም አንቃወማቸው” ያለው ማን ነበር?
ለነጻነት ሲባል ራሳቸውን ለመሰዋዕትነት የሚያቀርቡ ወገኖች የሚያምጹት ያለ ምክንያት አይደለም። በሁሉም ውስጥ ቁስል አለ!

↧

የሰላም ትግሉ በኢትዮጵያ (ክፍል ፬) –አንዱዓለም ተፈራ

$
0
0

አንዱዓለም ተፈራ/ የእስከመቼ አዘጋጅ

አርብ፤ ሐምሌ ፲ ቀን፤ ፳ ፻ ፯ ዓመተ ምህረት ( 7/17/2015 )

አሁን ካለንበት ወደፊት ለመሄድ ከየት እንጀምር? ( የመጀመሪያው ጉዳይ )

አሁን ሀገራችን ኢትዮጵያ ባለችበት የፖለቲካ ሀቅና የታጋዩ ክፍል በቆመበት መሬት፤ በር የሚያንኳኳና ደረስኩ የሚል ጥሪ መጥቷል። ትግሉን አብረን ማድረግ አለብን! እያለ። በያለንበት እንተባበር! እያለ። መቼም ይሄን የማይል ሕይወት የለም። ሁላችን እንፈልገዋለን። ሁላችን ትክክለኛና መሆን ያለበት ግዴታ ነው እንላለን። ሌላ አማራጭ እንደሌለ እናምናለን። ታዲያ ከየት እንጀምር? በክፍል አንድ፤ በአሁኑ ሰዓት የሰላማዊ ትግሉ በኢትዮጵያ ምን እንደሆነ ገልጫለሁ። በክፍል ሁለት ደግሞ፤ ስለሰላማዊ ትግሉ ያለንን ግንዛቤ አሳይቻለሁ። በክፍል ሶስት፤ ከዚህ ቀደም የሰላማዊ ትግል ካካሄያዱ ሌሎች ሀገሮች የምንማረውን ዘርዝሬያለሁ። በዚህ በአራተኛው ክፍል፤ ሶስት ጉዳዮች ያሉት ዘገባ አለኝ። የመጀመሪያው ጉዳይ፣ አሁን ካለንበት ወደፊት ለመሄድ ከየት እንጀምር? የሚለውን ራሱን በመመርመር፤ አጠቃላይ ሂደቱን እነድፋለሁ። ተከታትለው በሚወጡት የሁለተኛውና የሶስተኛው ጉዳዮች፤ በተጨባጭ በዝርዝር ማድረግ ያለብንን እዘረዝራለሁ።

ወደፊት ለመሄድ፤ መጀመሪያ ያለንበትን የፖለቲካ ሀቅ በትክክል ማወቅ፤ ግድ ይላል። ያለንበትን በትክክል ማወቁ፤ ለምናደርገው ጉዞ ትክል ማጠንጠኛው ነው። ይህ የኢትዮጵያ ሕዝብ፤ ከባርነት ለመውጣት የሚያደርገው የነፃነት ትግል ነው። ታጋዩም መሪውም ሕዝቡ ነው። ለዚህ የምንስማማባቸውን አስፍረን፣ ማድረግ ያለብንን ለይተን አቅርበን፣ የነገዋን ኢትዮጵያ ሕያውነት ገሀድ የማድረጉ ኃላፊነት የኛ ነው።

ለሁሉም እስኪ በመጀመሪያ የምንስማማባቸውን መሠረታዊ የሆኑ ዋና ሀገራዊ ሀቆች ላስፍር፤

፩ኛ.      በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ገዢ፤ እንደ ኢትዮጵያዊ ሳይሆን፤ እንደ ጠላት ወራሪ የሚገዛ ቡድን ነው፤ እናም ይህ መንግሥት መወገድ አለበት። ይህ መንግሥት ሕገወጥ ነው። ይህ መንግሥት አድሎዓዊ ነው። ይህ መንግሥት አምባገነን ነው። ሀገራችንን ወደ አደገኛ አዘቅት እየወሰዳት ነው። አስተዳደሩ በሙስናና በዘረኝነት የተወጠረ ነው። ረሃብና ድህነት እንደ ጥላ አብረውን የሚጓዙ ወዳጆቻችን በሆኑበት ሀቅ፣ ስደትና ከሀገር የነፍስ አውጭኝ ሩጫ በነገሡበት ሀቅ፣ ጥቂቶች ከምርጥ ዘር የመጡ ሁሉን በሚቆጣጠሩበት ሀቅ፣ ወጣቱ በሱሰኛ እጽዋት በተመረዘበትና ሥራ ባጣበት ሀቅ፣ ኢትዮጵያዊ መንግሥት አለ ብሎ መናገር፤ የሀገርን ትርጉም አላዋቂነትን ያሳያል። እናም ይሄን ለምናውቅ፤ ይህ መንግሥት መወገድ አለበት።

፪ኛ.      ይህ መንግሥት መወገድ ያለበት፤ በጠቅላላ በሕዝቡ ተሳታፊነት በተካሄደ ትግል ብቻ ነው። ሕዝቡ የድሉ ባለቤት የሚሆነው፤ ሕዝቡ በሙሉ “የኔ” ብሎ በአንድነት፣ ሀገራዊ ነፃነትን ባነገበ አንድ ድርጅት ሥር ታግሎ፤ ነፃ ሲሆን ብቻ ነው። ሀገራዊ ነፃነት፤ በሕዝቡ አንድነት ብቻ እንጂ፤ በድርጅቶች ጋጋት አይካሄድም። እናም በምንችለው ሁሉ ጥረታችን መሆን ያለበት፤ ይሄን የሕዝቡን በአንድነት የትግል መነሳሳት እውን ማድረግ ነው። በጭፍን ይሄን መንግሥት እንጣል ብቻ ማለት፤ የአንድነት ሀገራዊ ትግልን ባህሪይ አለመረዳትን ያሳያል። እናም ሕዝባዊ ትግሉ በአንድ ድርጅት ሥር መካሄዱ የግድ ነው። ሕዝቡን ተክቶ የሚታገል ፓርቲ የለም። በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ከመጠቀው የተማረው ወጣት አንስቶ፤ በቁጥር በብዙ ሚሊዮን እጥፍ ከሚበልጡትና የቴክኖሎጂን ጭላንጭል ሊያዩ ቀርቶ፤ የዕለት ምግባቸውን ከየት እንደሚያገኙ እስከ ጣጠራቸው የገጠር ዘመዶቻችን ድረስ፤ የዚህ ትግል ባለጉዳዮች ነን። ይሄን በተስተካከለ መንገድ እንዲሄድ ማድረግ እንችላለን። ዕውቀቱ፣ ልምዱና ችሎታው አለን። እያንዳንዳችን ኢትዮጵያዊ ነን የምንል ሁሉ፤ የዚህ ትግል ባለጉዳዮች ነን። ጥረት ማድረግ አለብን። በሌሎች ጫንቃ ላይ ልንንጠላጠል፣ ወይንም ሌሎችን አዝለን የድሉን ፍሬ ልንበላ አንችልም።

፫ኛ.      የሚቀጥለው መንግሥት ሲመሠረት፤ ሁሉን አቀፍና ጊዜያዊ መሆን አለበት። ላንዴም ለመጨረሻ ጊዜም ከጦርነት እሽክርክሪት ወጥተን፣ ኢትዮጵያዊ የሆነ መንግሥት እንዲኖረን፤ ከድል በኋላ መቋቋም ያለበት፤ የሽግግር መንግሥት ነው። ይህ የሽግግር መንግሥት፤ በትግሉ ላይ ከተሰማሩት የተውጣጣ ሆኖ፤ የሀገሪቱን ሕገ መንግሥት፤ ሁሉን አቀፍ በሆነ መንገድ፤ ከሕዝቡ በትክክል በመሰብሰብ፤ ያዘጋጅና ያቀርባል። በዚህ ወቅት ብዙ ሌሎች ጉዳዮች ይከናወናሉ። በተወሰነ ጊዜ የሚካሄድ የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ያዘጋጃል። ትክክለኛ ምርጫ ያካሂዳል። ለተመረጠው ክፍል ሥልጣኑን ያስረክባል።

እንግዲህ ይህ አሁን ላለንበት የትግል ሁኔታ፤ በሀራችን ላይ ያለና መሠረታዊ የሆነ፤ ሁላችን የምንስማማበት፤ የፖለቲካ ግንዛቤ ነው። እዚህ ላይ ልዩነት ካለ፤ ወደፊት መቀጠል አይቻልም። የትግሉ ባለቤት ከሆነው፤ ከሕዝቡ ጋር፤ እየታገለ ካለውና ለወደፊት ከሚቀላቀለው ጋር አብሮ ተደራጅቶ ለትግል መሰለፍ፤ ግዴታ ነው። ለየግላችን ድርጅት ፈጥረን፣ በራሳችን ድርጅት ሥር ብቻ በመሰባሰብና፣ ከሌሎች በየራሳቸው ድርጅቶች ከተሰባሰቡት ጋር በመተባበር ለመታገል መሞከር፤ መሠረታዊ የሆነውን የሀገር ጉዳይ፤ ከድርጅት በታች አድርጎ ማስቀመጥ ነው። በርግጥ በሁሉም ጉዳዮች ላይ፤ በግለስብም ሆነ በቡድን፤ አንድ አቋም ሊኖረንና ልንስማማ አንችልም። በዚህ ምንም ዓይነት ብዥታ ሊኖረን አይገባም። ሀገራችንን ከወገንተኛው አምባገነን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ነፃ ለማውጣት፤ መታገያችን በሆኑ መሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ግን፤ የግድ መስማማት አለብን። መሠረታዊ የሆኑት መታገያ ሀገራዊ ጉዳዮቻችን ምንድን ናቸው? መሠረታዊ የሆኑት መታገያ ሀገራዊ ጉዳዮቻችን፤ ከላይ በቁጥር ፩፣ ፪ትና ፫ ከሰፈሩትና ከምንስማማባቸው የፖለቲካ ሀቆች ይመነጫሉ።

፩ኛ.      በኢትዮጵያ ሀገራችን፤ ኢትዮጵያዊነታችንን አምነን የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን፤ በዚሁ በኢትዮጵያዊነታችን፤ አንድነታችንን እናንጠብቃለን። ኢትዮጵያዊያን አንድ ነን። በማንኛውም መንገድ ኢትዮጵያዊ ሆነን ስንገኝ፤ ያ ኢትዮጵያዊነታችን አንድና አንድ ብቻ መሆኑን እናስከብራለን። የተለየ ቦታ ያለው ኢትዮጵያዊነት አይኖርም።

፪ኛ.      የሀገራችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር አስከብረን፤ በግዛቷ ስፋት ውስጥ፤ ሁሉም መሬቷ ለኢትዮጵያዊያን እንዲውል አድርገን፣ አንድነቷን እንጠብቃለን።

፫ኛ.      እያንዳንዳችን ኢትዮጵያዊያን፤ በሀገራችን የፖለቲካ ጉዳይ ስንሳተፍ፤ በግል ኢትዮጵያዊነታችን ላይ ከመነጨ መብት ነው። የያንዳንዳችን የግለሰብ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲያዊ መብትን፤ ያለማዛነፍ እናከብራለን።

፬ኛ.      በሀገራችን በኢትዮጵያ፤ የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን እናደርጋለን። በሕግ ፊት የበላይና የበታች አይኖርም። ሁሉም ኢትዮጵያዊ፤ በሕግ ፊት እኩል እንዲሆን እናደርጋለን።

፭ኛ.      የኢትዮጵያ ሕዝብ ሉዓላዊነትን እናስከብራለን። ምን ጊዜም ቢሆን፤ በኢትዮጵያ ውስጥ፤ ሕዝቡ የመንግሥቱ ባለቤት እንጂ፤ መንግሥቱ የሕዝቡ ባለቤት የሚሆንበት ክስተት ያቆማል። የሕዝቡን የበላይነት እናከብራለን።

ከላይ የተዘረዘሩት አምስቱ መታገያ ሀገራዊ ዕሴቶቻችን ናቸው። እኒህ ግድግዳና ማገር ሆነው፤ ቤቱን የሚሸከሙ ናቸው። ጣራው ከላይ ይደረባል። ምርጉና ልሰናው ይከተላል። በነዚህ ዕሴቶቻችን ላይ መጨመር ይቻላል። ተጨማሪዎቹ ግን፤ ጊዜን ጠብቀው፤ ለነዚህ አምስት ዋና መታገያ ዕሴቶቻችን ተገዝተው ሲቀርቡ ነው ተቀባይነት የሚኖራቸው።

እንግዲህ እንደዚህ የተበታተነ ትግል በያዝንበት ወቅት፤ ለስምምነቱም ሆነ ለመለያየቱ መድረካችን አደባባዩ ሆኗል። በሚስጥርና በጓዳ የሚደረግ ስምምነትም ሆነ ልዩነት፤ አድሮ የራሱ አዛባ እየጠፈጠፈ፤ ብትንትናችንን ያወጣዋል። እናም ባደባባይ ይሁን መስማማታችን። ለሕዝብ የሚደረግ የሕዝብ ጉዳይ፤ ግልጽነት ግዴታው ነው። ከማን ይደበቃል። በማን ጀርባ ይንሾካሾካሉ? አይቻልም።

ትግሉ ተደራጅተው ለሚታገሉት ብቻ የተሠጠ፤ የግል ኃላፊነታቸው አይደለም። ይህ ሀገራዊ ትግላችን፤ “እኔ ስላልተደራጀሁ አያገባኝም!” ወይንም “ተጠያቂ አልሆንበትም!” ብዬ ላመልጠው አልችልም። ኢትዮጵያዊነቴን ካልካድኩ በስተቀር! እናም፤ ግለሰብ እና በድርጅት ያሉ የድርጅት አባላት እኩል ተጠያቂነት አለብን። ስለዚህ ጥረቱ ከሁላችን መሆን አለበት። ራስን ነፃ ለማውጣት፤ “ድርጅቶች እኮ አይረቡም!” “እነሱ መድረኩን አጣበው ይዘውታል!” እና ሌሎች ይኼን የመሳሰሉ ማምለጫ አባባሎች ተበልተዋል። አይሠሩም። መታገል ያለባት መሆኗን የተረዳች እህት፤ በግለሰብ ያለባትን ኃላፊነት ለመወጣት፤ ማድረግ ያለባትን የምትወስነው ራሷ እንጂ፤ ያሉ ወይንም የሌሉ ድርጅቶች አይደሉም። የድርጅቶች መኖር ወይንም አለመኖር፤ የአንድን ግለሰብ የትግል ፍላጎት፤ አያስሩም። ካልወደዳቸው፤ ሌላ መንገድ እንዲፈልግ ያስገድዱታል።

በተጨማሪም፤ ሌሎቹ አይረቡም በማለት የሚቀርበው ያለመስማማት መንገድ የትም አያደርስም። የኢትዮጵያን ሕዝብ ባንድ አቆራኝቶ ለማታገል የተነሳ ድርጅት ሆነ ግለሰብ፤ “ይሄ አንዲያ ነው!” ወይንም “ያቺ አንዲህ ነች!” “ያ ድርጅት እንዲያ ነው!” ወይንም “እነሱኮ . . .!”  በማለት ላለመተባበር ማምለጫ ማበጀት፤ ኃላፊነት የጎደለው አካሄያድ ነው። ደግሞስ ለምን በሁሉ ነገር ከሚስማሙን ጋር ብቻ እንሠራለን ብለን እንነሳለን? ይሄ እኮ የሀገር ጉዳይ ነው!  እንኳንስ በትግሉ የተሰማሩት ቀርቶ፤ ገና የገዠው ክፍል አባላት፤ ትግሉ ሲግልና መፈርጠጥ ሲጀምሩ፤ አቅፈን ከጉያችን እናሰልፋቸዋለን። የያዝነው ሀገራዊ ትግል ነው! ቁርሾ መወጫ ጨዋታ አይደለም።

ሰሞኑን በግብታዊነት ድርጅቶችን ለማስተባበር ጀምሬ ነበር። በርግጥ ትልቁ ስህተት ከኔ ነበር። ወደፊት እንዳሰብኩት አልሄደም። ከዚህ ጠቃሚ ተመክሮ ወስጃለሁ። በሂደቱ ብዙ ታጋዮች ድጋፍ አድርገውልኝ፤ እንዴት ሊተባበሩኝ እንደሚችሉ ሃሳብ ሠጥተውኛል። አብረውኝ ቆመዋል። አብረን ወደፊት እንሄዳለን። በጣም አመሰግናቸዋለሁ። የጊዜውን አጣዳፊነት፣ የአደጋዉን አስጊነትና የሁኔታውን አመቺነት ብቻ አንግቤ፤ ከእውነታው ይልቅ ፍላጎቴን አስቀድሜ ያደረግሁት ሩጫ፤ ፍሬ ሳይይዝ ቀረ። አምናለሁ፤ ይህ በአንድነት ተሳባስበን የመታገሉ ግዴታ፤ አብሮን አለ። የትል አልሄደም፤ አይሄድምም። ከኔ በፊት ሌሎች ጥረውበታል። አሁንም ሌሎች በሚችሉት እየጣሩ ነው። ጊዜ ይወስዳል። በትግሉ ብዙ የቆዩ አሉ። በትግሉ ብዙ የተማሩ አሉ። በትግሉ በተለያየ መንገድ፤ የተለያየ ግብ ይዘው የቀረቡ አሉ። እናም እኒህን ሁሉ በአንድ ማሰባሰቡ ቀላል አይደለም። ከተጨባጩ የሀገራችን የፖለቲካ ሀቅ በላይ፤ አስቸጋሪና ተጎታች የሚሆነው፤ በትግሉ ዙሪያ ያሉትን ወደ አንድ እንዲመጡ መለማመጡ፣ ማባበሉ፣ ማንቆለጳጰሱ፣ ማስጎምጀቱ፣ ማጓጓቱና መጎተቱ ነው። ከዚህ በተሻለ መንገድ አሁንም ሳላርፍ እቀጥላለሁ።

በተለያዩ ታጋይ ድርጅቶች ሥር ያሉት አባላት መረዳት ያለባቸው፤ በድርጅታቸው ሥር ያከናወኑት ሁሉ፤ እያንዳንዱ ድርጅት የፈጸመው በጎ ተግባር፣ ያከናወናቸው ትክክለኛ ጀብዱዎች፣ ጉድለት የታየባቸው ተመክሮዎችና በትግሉ የተሰዉ ጓዶቻቸው፤ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃነት ያደረጉት ስለሆነ፤ የየግል ድርጅቶች ታሪክ ሳይሆን የመላ ኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል አካል በመሆኑ፤ የየድርጅቶቻቸው ስም ቢቀየር፣ ድርጅቶቹ ቢፈርሱ፤ ይህ ታሪክ ቋሚ ሆኖ ይኖራል። እናም በአንድ እንሰለፍ ስንል፤ ይሄን ታሪክ ወደ አንድ አጠቃለን እናመጣዋለን እንጂ፤ ማንም ሊሠርዘው አይችልም። ትግሉ አንድ ነው። የኢትዮጵያዊያን የነፃነት ትግል ነው። አሁን የያዝነው፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግልና ታሪክ እንጂ፤ የድርጅቶች ትግል ወይም የድርጅቶች ታሪክ አይደለም። ከወራሪው የፋሽስቱ ጣልያን ጋር ተጋፍጠው የተሰለፉትን አርበኞቻችን፤ በአብቹ ተሰለፉ በበላይ ዘለቀ፤ አርበኞቻችን ብለን እናነሳቸዋለን እንጂ፤ የአብቹ አርበኞች ወይንም የበላይ ዘለቀ አርበኞች አንላቸውም። አሁን ያሉት ድርጅቶች መሠረታቸው፤ የአባሎቻቸው ቁጥር ብዛት፣ ያላቸው ታሪክ፣ ያካበቱት ንብረት ወይንም የመሪዎቻቸው ማንነት ሳይሆን፤ መርኀ-ግብራቸውና ርዕዩተዓለማቸው ነው። ያ ደግሞ ትርጉም የሚኖረው፤ ሕዝቡ የመምረጥ መብት ኖሮት፤ ከዚህኛው ያኛው ይሻላል ብሎ የሚያማርጥበት ወቅት ሲመጣ ነው።

ሁለተኛውን ጉዳይ በሚቀጥለው ጽሑፌ አቀርባለሁ።

ከታላቅ ምስጋና ጋር

eskemecheeske.meche@yahoo.com  http://nigatu.wordpress.com

↧

ትግሉን ከጫፍ ለማድረስ 3 ወሳኝ ነጥቦች –በሶሊያና ሽመልስ (Video)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ጋዜጠኛ ሶሊያና ሽመልስ ሰሞኑን በዋሽንግተን ዲሲ በተደረገ ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ትግሉን ከጫፍ ለማድረስ 3 ወሳኝ ነጥቦች በሚል ንግግር አድርጋ ነበር:: ሶሊያና በንግግሯ በተለይ ተቃዋሚዎች ስኬታማ ድል ማግኘት ከፈለጉ በጋራ የሚያግባባቸውን ነገር ፈልገው በርሱ ላይ መስራት ይኖርባቸዋል ስትል ትደመጣለች:: ሙሉውን ቭዲዮ ዘ-ሐበሻ በካሜራዋ ይዛዋለች – ይመልከቱት::

soliana Shimelis

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live




Latest Images