Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

”ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው”–ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

$
0
0

Birhanu Nega PHD
የአርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያቀረቡት አስቸኳይ ጥሪ

የተከበራችሁ ወገኖቼ፤ ከሰላሳ በላይ የሆኑ ወገኖቻችን አይ ሲስ በተሰኘ ህሊና ቢስ፣ ፀረ-ሰው እና ፀረ-ስልጣኔ ቡድን በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ የመገደላቸው መርዶ ከትናንት ወዲያ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓም ደርሶን ኢትዮጵያዊያን በያለንበት በመሪር ሀዘን ውስጥ ነን። ዛሬ “እግዜር ያጥናህ” ወይም “እግዜር ያጥናሽ” የሚባል ሰው የለም። ሁላችንም ሀዘንተኞች ነን። ካጣናቸው ቁጥራቸው በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ወገኖቻችን አሁንም በአራዶች መዳፍ ውስጥ መሆናቸው ሀዘናችን እጅግ የበረታ ያደረገዋል። ቁጥራቸው በትክክል የማይታወቅ ሆኖም በሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ዛሬም ሊቢያ ውስጥ ናቸው። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሁንም ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ናቸው። ሌሎች በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ደግሞ በየመን ከሰማይም ከምድርም በቦንብና በጥይት እየተማገዱ ነው።

ለምንድነው ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እሳት ውስጥ ለመማገድ የምንደፍረው? መልሱ ግልጽ ነው። አገር ውስጥ ተስፋ የለም፤ ወያኔዎች ተስፋችንን አጨለሙት። ከሳዉዲ በመከራ የተመለሱ ወንድሞቻችን ናቸው በሊቢያ በኩል ለመሰደድ ሲሞክሩ በአይ ሲስ ተይዘው የታረዱት። ወያኔዎች አገራችንና ክብራችን ዘረፉን። ወያኔዎች ስብዕናችንን ገፈፉን።

የዘመኑ ጥቂት የህወሓት ቱጃሮች ፎቆችን እየገነቡ በነሱ መጥገብ እኛ እንድናገሳላቸው ይፈልጋሉ። የኢትዮጵያ ሕዝብ መራቡ፣ መታረዙ፣ መደህየቱ እውነት ነው፤ ሆኖም ግን “ተራብኩ”፣ “ታረዝኩ”፣ “ደኸየሁ” ብሎ መናገር አይችልም። እውነት መናገር ያስቀጣል፣ ያስወነጅላል። በፍርደ ገምድል ችሎት እውነት መናገር “ሽብርተኛ” ያስብላል። እስር ቤቶችን የተሞሉት ለእውነት፣ ለፍትህ፣ ለነፃናትና ለእኩልነት በቆሙ ሰዎች አይደለምን?

በአይ ሲስ ያሳረደን ማነው? መልሱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ነው። ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው። እንደ አገርና እንደ ሕዝብ የደረሰብን ውርደት የትም ብንሄድ የምናመልጠው አልሆነም። በአገር ውስጥ የደረሰብንን ውርደት ለማምለጥ ስንሰደድ ውርደት ተከትሎን ይመጣል።

ወገኖቼ፤ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ የተሻለች አገር ሊኖረን አይችልም። ዛሬ የመሸሻ ጊዜ አይደለም። አገራችንን ከወያኔ ነጥቀን፤ በአገራችን ኮርተን በሰላም መኖር እንሻለን። ይህ መብታችን ነው። አገራችን የኛ ነች። አገራችን የጥቂት ወያኔዎች መፈንጫ አይደለችም።

ወገኔ፤ ዛሬ ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም በአርበኖች ግንቦት 7 ስም የማደርግልህ ጥሪ አድምጠኝ። በሀይማኖት፣ በብሔር፣ በጾታ ልዩነት ሳታደርግ ዛሬ በአንድነት እንደተሳህ አንድነትህን እንደጠበቅህ ቀጥል። አንድነትህን ለመሸርሸር ወያኔ የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም፤ ለወያኔ ዱለታ ጆሮህን አትስጥ። የወያኔ አገዛዝ እንዲያበቃ በአንድነት ተነስ። ዛሬ የጀመርከው ትግል እዳር ሳይደርስ እረፍት የለንም።

አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር በመጣመር የአገር አድን ኃይል የመገንባት ሥራውን እያጠናቀቀ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት ሳንከፋፈል፤ ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ባካተተ ስብስብ ውስጥ አብረን ህወሓትን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የአንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ነው። የትግሉም የአገሪቷም ባለቤት አንተ ነህ። ስለሆነም ተነስ! “እንቢኝ” በል። ዘርፈ ብዙ የትግል ስልቶችን በመጠቀም ወያኔን አዳክም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! በትግልህ ፍሬ የአገርህ ባለቤት ሁን።

የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። የደረሰብንን ብሔራዊ ውርደት እያያችሁ፤ እሮሮዓችን እየሰማችሁ በሕዝብ ላይ መተኮስ በራሳችሁ ጭንቅላት ላይ መተኮስ ማለት መሆኑን ለደቂቃ እንኳን አትዘንጉ። ይልቁኑ ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ።

የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ የወጣትነት የፈጠራ ችሎቻችሁ መፈተኛው አሁን ነው። ለእያንዳንዱ ጥቃቅን ጉዳይ መመሪያ እስኪሰጣችሁ አትጠብቁ። እያሰላችሁ፣ እያጠናችሁ፣ እያደባችሁ፣ ወያኔን ታገሉ።

የታፈረች፣ የተከበረችና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን።

ብርሀኑ ነጋ

የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር

ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም

The post ” ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው” – ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ appeared first on Zehabesha Amharic.


ከ መሬት ለባለሀብቱ ጀርባ ? –ኤድመን ተስፋዬ

$
0
0

comment picእ.ኤ.አ በ2007/08 በነዳጅ ሀብቱ እና በሀገሩ ያሉትን እህቶቻችንን እና ወንድሞቻችንን በማሰቃየት የሚታወቀው ሳውዲ አረቢያ መንግስት በንጉሱ ንጉስ አብዱላህ አነሳሽነት የሀገሩን ዜጎች ለመመገብ በሚል አዲስ መርሀ ግብር የነደፈ ሲሆን፣ በንጉሱ የተነደፈው የግብርና መርሀ ግብር አላማው መሬት በሚሸጡ ደሀ ሀገራት መንግስታት ላይ ትኩረት በማድረግ በነዚህ ሀገራት የሚገኙትን ለም መሬቶች በሳውዲ መንግስት ስም በሽያጭ እና ወለድ አግድ የመሬት ይዞታ(ንብረትን በግዥ፣በኮንትራት፣በሊዝ) ባለቤትነት በመያዝ አስፈላጊውን የመዋእለ ነዋይ ፍሰት በማድረግ በነዚህ ሀገራት የሚመረተውን የግብርና ምርት ወደ ሳውዲ በመላክ የሳውዲን ህዝብ መመገብ ነው፡፡ ይህ በአለማችን ላይ የሚገኙትን የዘመናችንን እውቅ ኢኮኖሚስቶች በሳተፈ መልኩ የተጠናው የሳውዲ አረቢያ የግብርና መርሀ ግብር ትኩረት የሚያደርገው በተለያዬ የውጪ ሀገራት ማለትም በኢትዮጲያ፣ሱዳን፣ዩክሬን፣ፊሊፒንስ እና ብራዚል በመሳሰሉት ሀገሮች ላይ ሰፋፊ መሬቶችን በመግዛት አልያም በመኮናተር ምርት አምርቶ ሳውዲ አረቢያን በእህል ምርት እራሷን ማስቻልን ላይ ነው፡፡ ይህንንም የሀገሪቷን አላማ የሳውዲ የንግድ እና ኢንደስትሪ ሚኒስትር በወቅቱ የመጀመሪያ አላማችን በውጪ ሀገራት የመሬት ይዞታ ንብረትን ማግኘት ሲሆን ቀጥሎም ዘመናዊ ግብርና ማስፋፋት በተያያዝም የመዋእለለ ንዋይ ፍሰት በማድረግ የመሠረተ ልማት መዋቅር በማስፋፋት የግብርና ምርቱን ወደ የሳውዲ ዓረቢያ መላክ እንደሆነ ዓላማቸውን በማስረገጥ ገልፀዋል፡፡ ከላይ በጠቀስኩት የሳውዲ መንግሰት አላማ መነሻነት በዋነኛነት የሳውዲ መንግስት ስም በተያዙ ትላልቅ የሀገራችን እርሻ መሬቶች ላይ የተመረተው ሩዝ እ.ኤ.አ ከ 2008 እስከ 2012 ወደ ሳውዲ የተጫነ ሲሆን በተጨማሪም ሀብቱ በሳውዲ ዜጋነት የተመዘገበው የቢሊየነሩ ሼህ መሀመድ አላሙዲን ድርጅት የሆነው የሳውዲ ስታር አግሪካልቸራል ዲቨሎፕመንት እና የህንዱ ካራቱሬ በሀገራችን ሰፋፊ የግብርና መሬቶችን በመውሰድደ የግብርና እንቅስቃሴ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

እንደ ዓለም ዓቀፍ የምግብና የእርሻ ድርጅት( Food and Agriculture Organisation (FAO) ጥናት ከሆነ ከኢትዬጵያ 145.6 ሚሊዬን ሄክታር ብዝሃ መሬት ውስጥ 100 ሚሊዬን ሄክታር ለእርሻ የሚሆን መሬት ሲሆን ይህም መሬት የሚታረሰው በአመዛኙ በአነስተኛ መሬት ባላቸው ገበሬዎችና ከእጅ ወደ አፍ በሆነ ገቢ በሚተዳደሩ ደሃ አርሶ አደሮች ሲሆን በጣም ትልልቅ የንግድ እርሻዎች ድርሻም 400,000 ሽህ ሄክታር መሬት ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2011 ኦክሰፋም ያወጣው ሪፖርት እንደሚያመለክተው የመካከለኛው ምስራቅና የሩቅ ምስራቅ ኢንቨስተሮች በታዳጊ ሀገራት ኢትዮጲያንም ጨምሮ ለያዙት የግብርና መሬት በሄክታር በአመት አንድ የአሜሪካ ዶላር (በአመት አስራ ዘጠኝ ብር አካባቢ መሆኑ ነው) ብቻ ነው የሚከፍሉት፡፡ በሀገራችንም ሆነ በሌሎች የአለማችን ሀገራት በውጪ ሀገራት መንግስታት ለግብርና ምርት በሚል የተያዘውን መሬት እንደ የአለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ሁማን ራይትስ ዎች እና ኦክስፋም ያሉ ተቋማት ከሀገሬው አርሶ አደር የመሬት ባለቤትነት እና መፈናቀል ወዘተ ጋር በተገናኘ ጉዳዩን በሀያ አንደኛው ዘመን የሚደረግ የመሬት መቀራመት መሆኑን በመግለፅ ክፉኛ ቢቃወሙትም የሀገራችንን መንግስት ጨምሮ መሬት ሻጭ የሆኑት መንግስታት መሬት መቸብቸባቸውን ቀጥለውበታል፡፡

የእውቁ ኢኮኖሚስት አዳም እስሚዝ የአለማቀፋዊነት ንድፈ ሀሳብ እንደሚያትተው በሀብት (በሰዋዊም ሆነ በቁሳዊ) ረገድ ሙሉ የሆነ የአለማችን ሀገር ባለመኖሩ ሀገራት በጎደለ ሙላ በሚለው መሰረት አንዱ ባለው ሀብት የሰውን ሀገር ቀዳዳ በመሙላት ቀዳዳውን ከሞላለት ሀገርም ሆነ ከሌሎች ሀገራት በሚያገኘው ሀብት (የገቢ እን የወጪ ንግድ ትርፍ) የራሱን ቀዳዳ በመሙላት የራሱን ሀገር ኢኮኖሚ ከማሻ|ሻል ባለፈ ለአለማቀፋዊ የኢኮኖሚ ትስስር መንስኤ ይሆናል፡፡ የወቅቱን በስግብግቦቹ ካፒታሊስቶች በሳፋ ተቀብሎ በማንኪያ መመለስ በሚል መርህ የሚዘወረውን አለማቀፋዊነት ወደ ጎን ትተን ይህን የአዳም ንድፈ ሀሳብ ከተመለከትነው የሚያመላክተን ፍትሀዊ ሆነ የኢኮኖሚ ሰጥቶ መቀበል መርህ የሚደረግ የሀገራት የኢኮኖሚ ሽርክና ከሀገራት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባለፈ ለአለም ሀገራት የኢኮኖሚ ትስስር መንስኤ የመሆኑን ሁነት ነው፡፡ የውጪ ሀገር መንግስታትም ሆነ ኩባንያዎች በሀገራችን መሬት ላይ ለዛውም የኢኮኖሚያችን የጀርባ አጥንት በሆነው ግብርና ላይ መሳተፋቸው በሀገራችን የግብርና ዘርፍ ላይ የሚፈጥረውን አሉታዊ እና አዎንታዊ ተፅእኖ የግብርናው እንቅስቃሴ በሚደረግባት ሀገራችን ያሉትን አርሶ አደሮች እና በሀገራችን የግብርና እንቅስቃሴ የሚያደርጉትን ሀገራት መነሻ በማድረግ ማየቱ ተገቢ ይመስለኛል፡፡

በዚህ መነሻነትም የውጪ ባለሀብቶች በሀገራችን መሬት ላይ የሀገራቸውን ህዝብ ለመቀለብ በሚል የሚያከናውኑት የግብርና እንቅስቃሴ በሀገራችን ግብርና ምርት እና አርሶ አደር ላይ ካለው ተፅእኖ አንፃር እና በውጪ ባለሀብቶች እየተከናወነ ያለው የግብርና እንቅስቃሴ በሀገራችን መንግስት ቢከናወን በሀገራችን ከሚያስገኘው ግብርናዊ ጥቅም አንፃር መመዘን ያስፈልጋል፡፡ በሌላ በኩል የምንገኝበት የሀያ አንደኛው ክፍለ ዘመን በሀገራት መሀል የሚደረግ ኢኮኖሚያዊ ሽርክና በሀገራቱ መሀል ካለው የኢኮኖሚ ሽርክና ባለፈ በሀገራቱ መሀል ባለ የፖለቲካ ሁነት እና ሀገራቱ ከሌላ ሶስተኛ ሀገራት ጋር ካላቸው ጤናማም ሆነ ጤናማ ካልሆነው የፖለቲካል ኢኮኖሚ ግንኙነት ተፅእኖ ስር የወደቀበት ዘመን መሆኑን የውጪ ሀገር መንግስታት በሰው ሀገር እያከናወኑት ያለው የግብርና እንቅስቃሴ ምክንያቱ ለሰው ልጅ የመኖር መንስኤ ለሆነው ምግብ ከመሆኑ ጋር ስንገምደው በሀገራችን የግብርና ምርት እያመረቱ ያሉትን የውጪ ሀገር መንግስታት በተለይ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራትን የወቅቱን የቀጠናውን የፖለቲካ ትኩሳት ማእከል ባደረገ መልኩ ሀገራቱ በሀገራችን የግብርና ምርት በማምረታቸው የተነሳ የወቅቱ የቀጠናው የፖለቲካ ትኩሳት ሀገራችን ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚያመጣውን አሉታዊ ተፅእኖ ሀገራቱ በሀገራችን የግብርና ምርት በማምረታቸው የተነሳ ለሀገራችን በቀጠናው ከሚፈጥርላት እና ከፈጠረላት ሀይል አንፃር በመመዘን ማየቱ ተገቢ ይመስለኛል፡፡

በሀገራችን መሬት ምግብ የሚሰራው የሳውዲ መንግስት እና የሀገራችን መንግስት

የሳውዲ መንግስት እንደ መንግስት በሀገራችን መሬት ላይ የራሱን ህዝቡ ለመቀለብ የግብርና ምርት ማምረቱ በራሱ ስህተት ያለው ይመስለኛል፣ እንደ እኔ እምነት ስህተቱ ያለው የሳውዲ መንግስት ይህን ያህል እርቀት ባህር አቋርጦ በሀገራችን መሬት የሚያመርትበት ምክንያት መንግስት ህዝቡን ለመቀለብ ምን ያህል ዋጋ እንደሚከፍል አሳይ መሆኑን እና የአለማችንን የዘመኑን የግብርና አመለካከት ያልተረዳው እና በውጪ ያሉትንም ሆነ የሀገር ውስጥ አቅሙ ያላቸውን ባለሀብቶች በማስተባበር እና ምቹ ሁኔታ በመፍጠር፣ በመንግስታዊ በጀት በሀገራችን የሳውዲ የሚያደርገው አይነት የግብርና እንቅስቃሴ (በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በሰፋፋ እርሻዎች ላይ) በማድግ የግብርና ምርቱን ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ በሀገራችን የሚታየውን የግብርና ምርት የዋጋ ንረት ማስወገድን ያልቻለው የሀገራችን መንግስት ላይ ይመስለኛል፡፡

በአዲስ አበባ ከሚተላለፉ የኤፍ ኤም ፕሮግራሞች በአንዱ ላይ የአየር ሰአት በነበረው የሰይፉ ፋንታሁን ፕሮግራም ላይ ሀብታቸው በሳውዲ ዜግነት የተመዘገበው ቢሊየነሩ ሼህ መሀመድ አላሙዲ ከሰይፉ ፋንታሁን ጋር ባደረጉት አጠር ያለ የስልክ ቃለ ምልልስ ሰይፉ ፋንታሁን እዚህ ብዙ የአርሰናል ደጋፊዎች ስላለን ለምን የአርሰናልን ክለብ አይገዙልንም ብሎ ለጠየቃቸው ጥያቄ ሲመልሱ የአርሰናልን ክለብ መግዛት ይቆየኝና አሁን (በጊዜው) ድርጅታቸው ግብርና ላይ ለመሳተፍ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን በመጥቀስ የግብርና ምርትን በሀገራችን ለማሳደግ እንደሚሰሩ መጥቀሳቸውን አስታውሳለው፡፡ በግብርና ላይ የተሰማራው የሼኩ ኩባንያ ሳውዲ ስታር አግሪከልቸራል ዲቨሎፕመንት በሊዝ ከወሰደው 24700 ሄክታር መሬት ውስጥ 860 ሄክታር መሬት ላይ ሩዝ በመዝራት ያገኘውን ጠቅላላ ምርት በተደጋጋሚ ወደ ሳውዲ መላኩን የኦክስፋም ሪፖርትን እና ዘ ሂንዱ በ ጁን 1/2013 የዘገበውን ዘገባ መነሻ ስናደርግ ሼኩ ቃላቸውን ጠብቀው የሀገራችንን ህዝብ በበቂ ሁኔታ የግብርና ምርት በገበያው እንዲያገኝ ሳይሆን ያደረጉት በሀገራችን መሬት ያመረቱትን ምርት ሀብታቸው ወደ ተመዘገበበት ሀገር ስለ መላካቸው የምንረዳ ይመስለኛል፡፡

የፖለቲካ አመለካከትን እንደ ቅድመ ሁኔታ የሚወሰድበትን ያልተፃፈ አሰራር ወደ ጎን በመተው በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ ያሉ አቅሙ ያላቸውን በተለይ በፖለቲካ የተነሳ ያላቸውን ሀብት በሰው ሀገር እያፈሰሱ ያሉትን የሀገራችን ዜጎች የሳውዲ መንግስትን ጨምሮ ሌሎች የውጪ ሀገር መንግስታት በሀገራችን መሬት እያመረቱ እንዳለው የሀገራችንን የግብርና ምርታማነትን በሚያሳድግ እና ለሀገር ውስጥ ፍጆታ ለሚውል የግብርና እንቅስቃሴ ላይ ተሳታፊ የሚሆኑበት አሰራር ቢኖር ኖሮ እና ቢዘረጋ በገዛ ሀገራቸው የሚኖሩትን ዜጎች በማፈናቀል እና ደን በመጨፍጨፍ የያዘውን መሬት የግብርና ምርት ሊያመርትበት ባለመቻሉ ለውጪ ሀገር ባለሀብቶች የሚሰጠውን የግብርና መሬት መጠን የሚጠቅሰው ፖሊሲ እንዲከለስ ምክንያት እንደሆነው እና ከሀገራችን ባንኮች የተበደረውን መመለስ እንኳ እንዳቃተው የህንዱ ካራቱሬ አይነት ድርጅቶች በሀገራችን መሬት ባልፈነጩ ነበር፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ኢኮኖሚያዊ አዋጭነታቸው እንደሀገር ምንም ባልሆኑ ነገር ግን ለሙስና ካላቸው ተመቻችነት አኩአያ ከፍተኛ በሆኑ እንቅስቃሴዎች ላይ ልማት በሚል የዳቦ ስም የሀገሪተዋን ሀብት የሚያፈሰው መንግስት የውጪ ሀገራት መንግስታት በሀገራችን ለህዝቦቻቸው ምግብ ዋስትና በሚል እንደሚያደርጉት በገዛ ሀገሩ መሬት ላይ እንደ እነሱ አይነት የግብርና እንቅስቃሴ በመንግስታዊ በጀቱ ለማድረግ አለመንቀሳቀሱ በአንድ በኩል የውጪ ሀገራት መንግስታት በሀገራችን መሬት ላይ የሚያደርጉት የግብርና እንቅስቃሴ ወደፊት ሀገራችን እያመረተች ወደ ውጪ የምትልከውን የግብርና ምርት በሀገራችን መሬት እያመረቱ በአለም ገበያ ተፎካካሪ የመሆናቸው አይቀሬነት ሲታይ በሌላ በኩል የመሬት ፖሊሲው፣የግብርና ግብአት (ማዳበሪያ በዋነኛነት) ብድር የግብርና እንቅስቃሴውን ሲኦል ያደረገበት የሀገሬ አርሶ አደር የራሱን የግብርና እንቅስቃሴ በመተው በውጪ ሀገራት መንግስታት እና ግለሰቦች ባለቤትነት ወደ ተያዙት እርሻዎች ተቀጣሪ ሆኖ የመስራቱ (እየሰራም ይገኛል) እድል ከፍተኛ የመሆኑ ሁነት ኢህአዴግ የስልጣኔ ምንጭም ሆነ የሀገራዊው ፖሊሲዬ ማእከል አርሶ አደሩ ነው ከሚለው ጋር ስንገምደው ኢህአዴግ እንደ መንግስት ግብርናው ላይ የሚከተለው ፖሊሲ ያስገኘውን ውጤት የዜሮ ብዜት የሚያደርገው ይመስለኛል፡፡

የሀገራችንን ኢኮኖሚ ከግብርና ወደ ኢንደስትሪ ለማሸጋገር በገዢው ፖርቲ የተነደፈው የአምስት አመቱ የእድገት እና የትራንስፎርሜሽን እቅድ አንድ አመት በቀረበት በያዝነው አመት ኦክስፋም በአለም ላይ ከሚገኙ ሀገራት በቂ የሆነ ምግብ የማይበሉ ህዝቦች ያሉባት ሀገር በሚል ከአለም ሀገራት በሁለተኛ ደረጃ ባስቀመጣት እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ለምግብ እጥረት የተጋለጡ ስድስት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ህዝቦች በዚህ አመት መኖራቸውን በገለጠባት ሀገራችን በግለሰብም ሆነ በመንግስት ደረጃ ሳውዲዎቹ በሀገራችን መሬት የራሳቸውን ህዝብ ለመቀለብ የሚያደርጉትን የግብርና እንቅስቃሴ ከኪራይ ከሚያገኘው አስቂኙ ገቢ በስተቀር በሁለትዮሽ ግንኙነትም ሆነ በተለዋጭ ጥቅም ሀገራችንን ተጠቃሚ ማድረግ ያቃተው እንዲሁም የሳውዲ መንግስት ከግብርናው እንቅስቃሴ ጋር በተገናኘ በሀገራችን ህዝቦች ላይ የሚደርሰውን የሰብአዊ መብት ጥሰት እና መፈናቀል በማስረጃ በማስደገፍ የሚያቀርቡትን አቤቱታ እንደ ለመደው የኒዮ ሊበራሊዝም አስተሳሰብ ውጤቶች በማለት ለሚያልፍው እና ሌላው ቢቀር እንደ መንግስት በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ ሙከራ ያላደረገው ኢህአዴግ ለውጪ መንግስታት ለግብርና በሚል የሰጠውን መሬት በተመለከተ የሚከተለው አካሄድ እንደ እኔ እምነት የራሷ አሮባት የሰው ቤት የምታማስለዋን ሴትዮ የሚያስታውስ ይመስለኛል፡:

ሳውዲዎቹ ለሀገራችን የሚያመጡት ትሩፋት ወይስ እዳ ?

ስለ ምድራችን የ ተፈጥሮ ሀብት እና ስነምህዳር የኢኮኖሚክስ አስተምህሮት ንድፈ ሀሳብ እንደ የሚነግረን እንደ የፀሀይ ብርሀን እና ዝናብ የመሳሰሉትን ተፈጥሮአዊ ሀብቶች ገንዘብ ሊገዛቸው አንደማይቻለው ነው፡፡ አሁን ላይ ምድራችን ያጋጠማትን የውሃ እጥረት፣የበረሀ መስፋፋትን ተከትሎ በአለም አቀፍ ደረጃ ያጋጠመው የምግብ እጥረት እና የምግብ ፍጆታዎች የዋጋ መናር መልካምድራዊ በሆኑ ምክንያቶች የተነሳ ለምግብ ፍጆታ የሚሆኑትን የግብርና ምርቶች በሀገሯቸው በበቂ ሁኔታ ለማያመርቱ እና ፍጆታዎቻቸው ከውጪ ሀገር ለሚያስገቡ ሀገራት ሁኔታው አስደንጋጭ ሲሆን፣ ይህ አስደንጋጭ አደጋ ከተጋረጠባቸው ሀገራትም ውስጥ አንዷ በነዳጅ ሀብቷ የምትታወቀው ሳውዲ አንዳ ስትሆን፡፡ ሀገሪቷ ይህን አደጋ ለመወጣት በነደፈችው የግብርና እቅድ መነሻነት እ.ኤ.አ በ2009 በሳውዲ አረቢያ ንጉስ አብዱላህ መሪነት በ መቶ ሚሊዮን ዩኤስ ዶላር የመዋእለ ነዋይ ፍሰት በሀገራችን መሬት የግብርና ምርት ማምረት የጀመረው የሳውዲ መንግስት በጋምቤላ ክልል በስሙ በተያዙ ሰፋፊ መሬቶች ያመረተውን የሩዝ ምርት እ.ኤ.አ ከ 2008 እስከ 2012 ወደ ሳውዲ የጫነ ሲሆን፣ ይህ በሀገራችን የተመረተው የሩዝ ምርት የሀገሪቱን የምግብ ክፍተት ከማጥበቡም በላይ ለሀገሪቱ የምግብ ፍጆታ ዋስትና በሚል በንጉሱ ለተነደፈው እቅድ እንደ ስኬት ተወስዳል፡፡

ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚ ግብአት ከሆኑት ውስጥ አንዱ የሆነውን የነዳጅ ሀብት የተጎናፀፈችው ሳውዲ በሀገራችን ለምግብ ፍጆታዋ የግብርና ምርት ማምረቷ ከሁለትዮሹ ሀራዊ ግንኙነት አኩአያ ከሚያስገኘው ጥቅም አንፃር ሲታይ በአጭር ጊዜም ይሁን በረዥም ጊዜ ለሀገራችን የነዳጅ ፍጆታ ፍላጎት ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ ባይሆን እንኳ ከበፊቱ በተሸለ ሁኔታ ዋስትና እንዲኖራት፣ለሀገራችን ዜጎች ምቹ ያልሆነውን የመሀከላው ምስራቅ ከበፊቱ በተሸለ ሁኔታ ለስራ ወደ አካባቢው በሚሄዱት ዜጎቻችን ላይ በተለይ በእህቶቻችን ላይ የነበረውን መጎሳቆል እንዲቀር መንስኤ ሊሆን በተቻለው ነበር፣ ነገር ግን ከሳውዲ መንግስት ጋር የሀገገራችንን መሬት በተመለከተ ውል የፈፀመውን የኢህአዴግ መንግስት ለትችት በዳረገው በቅርቡ በሳውዲ ሀገር በእህቶቻችን ላይ የተፈፀመው አረመኔአዊ ተግባር ባጎረስኩኝ እጄን ተነከስኩኝ አይነት መሆኑ ውሉ ከሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ላይ ያለውን ሀገራዊ ጠቄሜታ ጥያቄ ውስጥ የሚከተው ይመስለኛል፣ በሌላ በኩልም በመሀከለኛወ ምስራቅ ቀጠና አሁን ላይ ለሚታየው የሶሪያ እና የኢራቅ ትኩሳት መንስኤ ለሆነው እና አላማው ቀጠናውን በፅንፈኛ አስተሳሰቡ አንድ አርጎ መምራት ለሆነው አይሲሲ የሎጀስቲክ እና የገንዘብ ምንጭ ነው በማለት በኢራን እና በሶሪያ የሚከሰሰው የ ሳውዲ መንግስት ህዝቡን ለመቀለብ በሀገራችን መሬት ላይ በሚያመርተው ምርት የተነሳ በፅንፈኛው አይሲሲ ሀገራቸው እየተመሰቃቀለ ያሉት ሀገራት እና ጉዳዩ ያሳሰባቸው ከቀጠናው ውጪ ያሉ ሀገራት ሀገራችን ላይ በቀጥታም ይሁን ቀጠተኛ ባልሆነ መንገድ ተፅእኖ ማድረጉ ቢኖር እንኳ በዲፕሎማሳዊውም ሆነ በሌሎች መንገዶች ረገድ እንደ መንግስት ተፅእኖውን ለመቋቋም ያለውን አቅም እና ተነሳሽነት በሳውዲ መንግስት በራሱ ዜጎች ላይ ለተፈፀመው ኢሰበአዊ መከራ ኢህአዴግ መራሹ የሀገራችን መንግስት ያከራየውን መሬት (ከሳውዲ ጋር ያለን የሁለትዮሽ የኢኮኖሚ ግንኙነት ወደ ሳውዲ ያደላ እና የሳውዲ መንግስት ኢኮኖሚያዊው ድጋፍ ከፈተኛ ቢሆንም አሁን ላይ ካለው የሳውዲ አንገብጋቢ የምግብ ፍጆታ ፍላጎት አኩአያ ያከራየናቸው መሬት ከፍተኛ አቅም ለሀገራችን መፍጠር ይችላል) ለተፅእኖ ያለመጠቀሙን እውነትነት ሲታይ ለሀገራችን አደጋ መፍጠሩ አይቀሬነት ማመላከቻ ይመስለኛል፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ በአሁን ዘመን በአለማችን እየተስፋፋ ያለውን የሀይማኖት አክራሪነት ባልተለመደ መልኩ እንስሳዊ በሆነ መንገድ ሰይጣናዊ አላማውን ለማሳካት ከሶሪያ እስከ ኢራቅ ከኢራቅ እስከ ሊቢያ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው እና የቀጠናውን ሀገራት በአንድ መንግስት የማስተዳደር አላማ ያለውን አይሲሲ በመርዳት የሚከሰሰው የሳውዲ መንግስት በሀገራችን መሬት በሚያመርተው ምርት የተነሳ የፅንፈኛው ተቃዋሚ የሆኑ ሌሎች አክራሪ ሀይሎችም ይሁን አይሲስ ላይ ጦርነት ያወጁ ሀገራት ሀገራችን ላይ ጥርስ ስለ አለመንከሳቸው መተማመኛ እንዳናገኝ በሀገራችን መሬት የግብርና ምርቶች እያመረተ የሚገኘው የሳውዲ መንግስት መንስኤ የሚሆን ይመስለኛል፡፡

The post ከ መሬት ለባለሀብቱ ጀርባ ? – ኤድመን ተስፋዬ appeared first on Zehabesha Amharic.

“በጆሮ እንደሰማን በአይን አየን”–አባ ወልደ ትንሣኤ አያልነህ

$
0
0

“በጆሮ እንደሰማን በአይን አየን”
በሐዲስ ሃዋርያ አባ ወልደ ትንሣኤ አያልነህ
በሊብያ በሰማዕትነት ላረፉትና በስቃይ ላይ ላሉ ወገኖቻችን የፀሎት ምሽት
በደብረ ፅዮን ድንግል ማርያም ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ካቴድራል Los Angles, CA

 

 

The post “በጆሮ እንደሰማን በአይን አየን” – አባ ወልደ ትንሣኤ አያልነህ appeared first on Zehabesha Amharic.

የማለዳ ወግ ቅምሻ ልዩ ዘገባ …”የISIS ሽብር እርምጃ አንድ አደረገን እንጅ አልለያየንም! “

$
0
0
(Photo File)

(Photo File)

* በሳውዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የአሸባሪው የ ISIS የእጭካኔ እርምጃ አዎገዙ !

* ” የሰው አራዊቶች እርምጃ ለዘመናት ተፋቅሮ ሳይለያይ የኖረው ኢትዮጵያዊ ሙስሊምና ክርስትያኑን አይለያየንም !” ከነዋሪው ድምጽ
* በሳውዲ ሰማይ የኢትዮጵያ ሀዘን ለመግለጽ ባንዴራችን ዝቅ ብሎ በመውለብለብ ላይ ነው
* የተለያዩ ሀገር ዲፕሎማቶች ሀዘናቸውን እየገለጹ ነው
* አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤት 3000 ተማሪዎች በሊብያ ለተሰውት ወገኖች የህሊና ጸሎት አድረጉ
* የውጭ ዲፕሎማቶችና ነዋሪው ጥልቅ ሀዘኑን በመግለጽ ላይ ናቸው
* መንግስት በሀገር ቤት ሀዘናቸውን ለመግለጽ በወጡ ወገኖች ላይ የወሰደው የሃይል እርምጃም ተኮንኗል

በማለዳ ወግ ሰሞነኛ የመረጃ ቅምሻ ፣ በአዲስ አቀራረብ በድምጽ የተሰናዳ ልዩ ጥንቅር … !

የሞቱትን ነፍስ ይማር !

ነቢዩ ሲራክ
በጨለመው ሚያዝያ 16o ቀን 2007 ዓም

The post የማለዳ ወግ ቅምሻ ልዩ ዘገባ …” የISIS ሽብር እርምጃ አንድ አደረገን እንጅ አልለያየንም! “ appeared first on Zehabesha Amharic.

በሚኒሶታ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የሻማ ማብራት ምሽት አካሄዱ * ከ10 በላይ የተለያይይ የሃይማኖት መሪዎች ተገኝተዋል (+Photo + Video)

$
0
0

Minnesota 1

Minnesota 2

Minnesota 3

Minnesota 4

Minnesota 5

Minnesota 6

Minnesota 7

minnesota 9

Minnesota 11

Minnesota 13

Minnesota 15

minnesota 18

Minnesota 19

Minnesota 20

Minnesota 21

Minnesota 22
(ዘ-ሐበሻ) አይሲኤል በሊቢያ 28 ኢትዮጵያውያን አርዶ እና በጥይት ከገደለ በኋላ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውን ከዳር እስከ ዳር ተቆጥተዋል:: ትናንት ማምሻውን ሐሙስ በመላው ዓለም ኢትዮጵያውያን በየሚኖሩበት ሃገር የሻማ ማብራት እና የጸሎት ስነ-ስርዓት አካሂደዋል::

በሚኒሶታ ስቴት ካፒቶል ደጃፍ ዘ-ሐበሻ እና የኢትዮጵያ ኮምዩኒቲ በመተባበር የጠሩት የሻማ ማብራት የመታሰቢያ ምሽት ላይ በሊቢያ… በደቡብ አፍሪካና በየመን የተገደሉ እና እየተሰቃዩ ያሉ ታስበዋል::

ከአንድ ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ኤርትራውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በተገኙበት በዚህ የመታሰቢያ ምሽት:-

– ከደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ መላከ ሰላም – ቀሲስ መሪጌታ ጌታሁን
– ከደብረብርሃን ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ – አባ ገብረኪዳን ገብረዋሂድ
– ጠሃ ሳሚር ከሪሳላ ኢንተርናሽናል የሙስሊም ማዕከል
– ናስር ሃምዛ ከቶፊክ ሙስሊም ሴንተር
– ፓስተር መልካሙ ነገሪ ከኦሮሞ ኢቫንጀሊካል ቤተክርስቲያን
– ፓስተር ፍራንሲስ ከኢትዮጵያ መካነኢየሱስ
– ፓስተር ስለሺ ከኢግል ክርስቲያን ቤተክርስቲያን
– ፓስተር አበባየሁ አበበ ከጎስፕል አማኞች ቤተክርስቲያን
– ፓስተር ደስታዬ ክራፎርድ ከኤቨንት ትራይብ ቤተክርስቲያን
– ወንድም ዳንኤል ከኤቨንት ትራይብ ቤተክርስቲያን
– የሴናተር ኬዝ አሊሰን ተወካይ
– የሴናተር ኤሚ ክላባቸር ተወካይ
– ወጣት ዛኪር ሃሰን
– ወጣት ቃልኪዳን አለማየሁ
– የኤርትራ ኮምዩኒቲ ተወካይ
– ወ/ሪት ዘመን ታደሰ
– አቶ ተከስተብርሃን ተፈራ
– ወጣት መስፍን አየለ
– አልዩ ተበጀ ከኢትዮ-ሲሊዳሪቲ ሚኒሶታ ግሩፕ

ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም በሊቢያ የተገደሉትን ኢትዮጵያውያን አስታውሰው በአይሲስ ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ተቃውሞ አሰምተዋል:: በደቡብ አፍሪካ እና በየመን እያለቁ ስላሉት ኢትዮጵያውያንም ተጸልይዋል:: ሁሉም የሃይማኖት መሪዎች ያሰመሩበት አንድ ነገር ቢኖር “አንድነት”ን ሲሆን ሁሉም አንድ ሆኖ ለሃገሩና ለሕዝቡ እንዲቆም ጠይቀዋል::

በሚኒሶታ ስቴት ካፒቶል በኢትዮጵያውያኑ መካከል የእምነት ልዩነት ሳይኖር በአንድ ላይ እንዲህ ያለው ትልቅ ዝግጅት መደረጉ ብዙዎችን ያስደሰተ ሲሆን ይህ መተባበርና አንድ መሆን በችግር ጊዜ ብቻ ሳይሆን በደስታውም ጊዜ አንድነቱ እንዲቀጥል ሕዝቡ ጠይቋል::

(የዚህን ዝግጅት ሙሉ ቭዲዮ እስከምንለቅላችሁ ድረስ ቀንጨብ ያለችውን የ5 ደቂቃ ቭዲዮ ይመልከቱ)

The post በሚኒሶታ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የሻማ ማብራት ምሽት አካሄዱ * ከ10 በላይ የተለያይይ የሃይማኖት መሪዎች ተገኝተዋል (+Photo + Video) appeared first on Zehabesha Amharic.

የሃዘኑ ድባብ በዱላ ታጅቦ…ክንፉ አሰፋ

$
0
0

  የሃዘኑ ድባብ ከመብራቱ መቆራረጥ ጋር ተዳምሮ ጨለማውን አብሶታል። የአሁኑ መብራት መቋረጥ ግን ከወትሮ ፈረቃ ለየት ያለ ነው። ሆን ተብሎ የተደረገ ይመስላል። ከጥቂት ስፍራ በስተቀር ሁሉም ቦታ በአንዴ እንዲጠፋ ነው የተደረገው። ከሬድዋን  ሁሴን እና ከሃይለማርያም የቴሌቭሽን ዲስኩር በኋላ ሃገሩ ሁሉ ጨለማ እንዲሆን አደረጉ። ይህንን ለማድረግም በቂ ምክንያት ነበራቸው። ሃዘን ያልወጣለት ህዝብ አደባባይ ወጥቶ በአረመኔ ወታደሮች ሲቀጠቀት በማህበራዊ ድረ-ገጽ እንዲታይ አልተፈለገም።  ህዝቡ እርስበርስ መረጃ እንዲለዋወጥ መፍቀዱም አደጋ አለው። ስልኩም ጠፋ!

TPLf 3

          ለጥቂት ጉልበተኞች ግን ይህ መብራት ከቶውንም አይጠፋም። ግዜው እስኪደርስ፣ የሚመኩበት ጉልበታቸው እስኪፈታ ድረስ ይበራል። እስከዚያው ብዙሃኑ በጨለማ ይኖራሉ። 

          የአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ንግግር ግን ከቴድሮስ አድሃኖም ጋር ትንሽ የሚጣረዝ ይመስላል። ድህነታችን ለስደት እንደዳረገን ነበር ሃይለማርያም በአደባባይ ይናገሩ የነበረው። ተሳስተው ነው? ወይንስ በጥድፍያው ምክንያት አልተናበቡ ይሆን? ልማታዊ መንግስት ድህነት የምትለዋን አይጠቀምም።  ቴዎድሮስ አድሃኖም ግን በፌስ ቡክ ገጻቸው  “ሁላችንም ወያኔ ነን” አዎ አሁንም ሁላችንም ወያኔን ነን። ወያኔነት ልማት፣ ኩራትና ዴሞክራሲ ነው።..ይህን ችግር የሚፈታውም ወያኔነት ነው!” ብለውናል። በመስቀል አደባባይ ወታደራቸውን አሰልፈው የሰላማዊውን ህዝብ ሃዘን በወያኔነት ሲመልሱትም አሳዩን።  በሊቢያ፣ በየመን እና በደቡብ አፍሪካ በሰቆቃ ያሉ ወገኖች የሚሉትንም እየሰማን ነው። “የኛ የምንለው መንግስት የለንም! … ጨለማ ውስጥ ሆነን እየጸለይን ነው።”  ይህ ነው የወያኔነት ወጤት።   

          አቶ ሃይለማርያም ተሳስተው አንድ እውነት ተናገሩ። አንድ ነገር ቢጨምሩበት ጥሩ ነበር። ለስደቱ መንስኤ የፍትሃዊ ስርዓት እና ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል መጥፋቱ መሆኑን። ለማንኘውም በውስጥ ግምገማ ላይ ይህችን ለምን እንደተናገሩ ያስረዱ ይሆናል።

          ለሃዘን የወጣ ህዝብ በአረመኔ ወታደሮች ሲቀጠቀት ሮይተርስ ከአዲስ አበባ አሳይቶናል። ዜጎች ሲቀጠቀጡ የሚያሳዩ የቪድዮ ምስሎች በማህበራዊ ድረ-ገሶች በስፋት ተበትነዋልል። ሬድዋን ሁሴን ግን ወታደሮቹ አንድም ሰው እንዳልነኩ ነገሩን። ታድያ ዥጉርጉሩን የፌዴራል ልብስ ያጠለቀ አይሲስ ነበር እንዴ በመስቀል አደባባይ ህዝቡን ሲያሸብር የነበረው?  ሃፍረት ያልፈጠረባቸው፤ የሰብአዊ ፍጡር ህሊና የሌላቸው ውሸታሞች ናቸውና ይህን ማለታቸው አይደንቅም።  ኢውሮ ኒውስ ከአዲስ አበባ በቀጥታ ያሳይ የነበረው ትእይንት ዘግናኝ ነበር። አይሲስ በንጹሃን ዜጎች ላይ የፈጸመውን የማይተናነስ ጭካኔ አሳዩን። ህጻን፤ ሴትና አዛውንት እንኳን ሳይለዩ ሁሉንም በጭካኔ ቀጠቀጡ።  የህዝብ ወገን ቢሆኑ በወገን፤ ለዚያውም በሃዘን ላይ ያለ ህዝብ ላይ እንዲህ አይጨክኑም። በእውነቱ ባእዳንም እንዲህ ባዘነ ህዝብ ላይ አይጨክኑም።  የ97ቱን ሰቆቃ አስታወሱን።   

          የታፈነው ህዝብ በአንድ ላይ ሆኖ ብሶቱን ሲገልጽ ሰማን።  ሬድዋን ሁሴን እንደሚሉት ከዚህ ረብሽ ጀርባ ሰማያዊ ፓርቲ አለበት። ከጨርቆስ እስከ ፈረንሳይ ለጋሲዮን፣ ከቦሌ እስከ ኮልፌ፤  ከዘነበወርቅ እስከ ሽሮ ሜዳ … ያለ  ህዝብ ሁሉ ሰማያዊ ፓርቲ ከሆነ ህዝብ ከናንተ ጋር አይደለምና ስልጣኑን ለሰማያዊ ፓርቲ ማስረከብ ነው ያለባቸው። አይገባቸው ይሆናል እንጂ በተዘዋዋሪ እየነገሩን ያሉት ህዝብ በሙሉ እንደጠላቸው ነው። ጥቂት ያሉትንም የህዝብ ቁጥር በምስል አየነው። 
tplf 2
          ይህ የህዝብ መልእክት ትምህርት ካልሆናቸው አምሯቸው የታወረ ነው። ክስተቱ እንደፈርዖን በባርነት የያዙት ህዝብ ምን ያህል እንደተከፋ ያሳየናል። 23 አመታት በጫንቃው ላይ የተቀመጠው ስርዓት ምን ያህል እንዳንገፈገፈው የሚያሳይ ባሮ ሜትር ነው።   

          ለመሆኑ እነዚያ ባለስልጣናት ሲሞት ደረት የሚመቱት ልማታዊ አርቲስቶች የት ጠፉ? “ታላቁ መሪ” ባረፉ ግዜ ማቅ ለብሰው እዩኝ-እዩኝ ይሉ የነበሩ አርቲስቶች ነብስ እየመረጡ ነው የሚያለቅሱት? በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ የተሰውት ወገኖች የሰብአዊ ፍጡራን አይደሉም እንዴ?  ወይንስ ሃዘንም በትእዛዝ ሆነ? መቼም በዚህ ሰቆቃ ለማዘን የግድ ኢትዮጵያዊ መሆን አያስፈልግም። ለማዘን ሰው መሆን ብቻ ይበቃል። በዚህ የጨለማ ወቅት ከህዝብ ወገን ያልሆነ ሁሉ ለህሊናው ሳይሆን ለሆዱ የሚገዛ እንስሳ ብቻ ነው። መቼም የማያልፍ ነገር የለም ይህም ያልፍና ሁላችንንም ያስተዛዝበናል።   

The post የሃዘኑ ድባብ በዱላ ታጅቦ… ክንፉ አሰፋ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢህአዴግ የሞቱትን ወገኖች ክብር እያራከሰ ነው ሲል ሰማያዊ ወቀሰ • ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ጉዳዩን በዝምታ አያልፈውም›› አቶ ዮናታን ተስፈዬ

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) ኢህአዴግ አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም በሚል በሚጠራቸው ሰልፎች ሰማያዊን በማውገዝ ላይ መጠመዱንና ይህንም ሰማያዊ ፓርቲ በዝምታ እንደማያልፈው የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ትናንት ሚያዝያ 15/2007 ዓ.ም በባህርዳር፣ ሆሳና እና ሌሎች የሀገሪቱ ከተሞች መንግስት በጠራው ሰልፍ ሰልፈኞቹ አይ ኤስን ሳይሆን ሰማያዊ ፓርቲን የሚያወግዙ መፈክሮችን ይዘው እንደወጡ የታወቀ ሲሆን አብዛኛዎቹ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ደም ከማፋሰስ ተግባሩ መቆጠብ አለበት›› የሚሉ መፍክሮችን ይዘው ወጥተዋል፡፡
ethiopian killed by isil 1
ይህ የሆነው አዲስ አበባ ውስጥ መንግስት የጠራው ሰልፍ ላይ ሰልፈኞች መንግስት ለችግሩ አፋጣኝ ምልሽ አልወሰደም በሚል ተቃውሞ ካሰሙ በኋላ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን ገና ፖሊስ ምርመራውን ሳይጨርስ ተቃውሞውን ያሰማው ሰማያዊ ፓርቲ ነው ብለው ከወነጀሉ በኋላ ፓርቲያቸው የያዘው አቋም እንደሆነ ኃላፊው ገልጾአል፡፡ አቶ ዮናታን ይህን የኢህአዴግ አቋምም ‹‹እጅግ አሳፋሪና አፀያፊ ነው›› ብሎታል፡፡ የባህርዳርና የሆሳና ሰልፈኞች ሰማያዊ ፓርቲን ለማውገዝ በያዟቸው መፈክሮች ፊታቸውን እንደሸፈኑ የገለፀው አቶ ዮናታን ሰልፈኞቹ በኢህአዴግ ተገድደው እንጅ አምነውበት እንዳልወጡ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

መንግስት ለችግሩ አፋጣኝ መፍትሄ መስጠት ሲያቅተው የሚነሱበትን ተቃውሞዎች ሰማያዊ ፓርቲና ድምጻችን ይሰማ የፈጠሯቸው አድርጎ መወንጀሉ ለስርዓቱም ሆነ ለሀገሪቱ አደጋ የሚፈጥር ነው ያለው አቶ ዮናታን ለአይ ኤስ አይ ኤስ ተብሎ የተጠራውን ሰልፍ ለራሱ የፕሮፖጋንዳ ፍጆታ ማዋሉ የሞቱትን ወገኖቻችን ክብር የሚያረክስ፣ ርካሽና ፀያፍ ፕሮፖጋዳ ነው ሲል ወቅሷል፡፡
ኢህአዴግ እንደ መንግስት መስራት ያለበትን ባለመስራቱ የሚነሱበትን ተቃውሞዎች ለመሸፈን እና አጀንዳ ለማስቀየስ ሲል በሰማያዊ ላይ እየፈጠራቸው ያሉትን ውንጀላዎች ፓርቲው በዝምታ እንደማያልፋቸውና ክስ እንደሚመሰርትም አቶ ዮናታን ገልጸዋል፡፡

The post ኢህአዴግ የሞቱትን ወገኖች ክብር እያራከሰ ነው ሲል ሰማያዊ ወቀሰ • ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ጉዳዩን በዝምታ አያልፈውም›› አቶ ዮናታን ተስፈዬ appeared first on Zehabesha Amharic.

ባለቤት ያጣ ትውልድ እንደ በግ ሲታረድ –በዲያስፓራ የዓረና ትግራይ ድጋፍ ከሚቴ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ

$
0
0

arenaበተወለዱባትና እትብታቸውን በተቀበረባት እናት ምድር ላይ እንደ ሰብኣዊ ፍጡር – እንደ ዜጋ በነፃነታቸው፣ በማንነታቸውና በኢት}ዮያዊነታቸው ኮርቶውና አልሞቶው በሰላም የመኖር አማራጭ ያጡና ተስፋው የጨለመባቸው ወገኖቻችን ሳይወዱ በግድ ስደት በመምረጥ መድረሻ አጥተው ሲንከራተቱና የሞት ፅዋን ሲቀበሉ የሚያሳይ በሊቢያ፣ በደቡብ አፍሪቃ፣ በሜዲተራኒያን ባህርና በየመን አካባቢ የደረሰባቸውን ዘግናኝና ልብ ሰባሪ ዜና ስንመለከት በዘመናችን ታይቶ የማይታወቅ እጅግ አስደንጋጭ በመሆኑ በጣም አዝነናል ተቆጥተናልም::

ኢትዮ}ያ ለዘመናት የነፃነት፣ የኩሩ ህዝብና የጀግና ሀገር ተምሳሌት እየተባለች በዓለም ማሕበረሰብ ዘንድ ወርቃማ ታሪክ ይዛ ተከብራና ታፍራ እንዳልቆየች ሁሉ ዛሬ ግን ገፀ ባህሪዋንና የነፃነት ድባብዋን በሀዘን ጨለማ ተቀይሮ ረሃብ፣ ስደት፣ ሞት፣ ውርደትና እልቂት የነገሠባት፣ ባለቤት ያጣች፣ የልቅሶና የዋይታ ምድር ሆና ስናያት በጣም ያሳዝነናል:: ይቆጨናልም::

ጨዋ፣ ኩሩ፣ እንግዳ አክባሪና የዋሁ ህዝባችንም ሀገርና መንግስት እንደሌለው ተቆጥሮ የውሻን ያህል እንኳን ክብር ሳይሰጠው እንደ በግ እየታረደ፣ እንደ ቆሻሻ ባህር ውስጥ እየተወረወረ፣ ከቦታ ቦታ በመንከራተትና እስር ቤት በመታጎር በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ የሚያነሳው ያጣ፣ የተዋረደና የረከሰ ህዝብ ሆኖ ስናይ እጅግ የሚያሳዝን የትውልድ ሐፍረት ነው::

በቅርቡ ከሳውዲ ዓረቢያ ወደ ሩብ ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎቻችን ከሰብኣዊ ርህራሄ አያያዝ ውጭ በጭካኔ ተደብድበውና ተዘርፈው ባዶ እጃቸውን በተባረሩበት ወቅት የደረሰባቸው የስነ ልቦና፣ የማሕበራዊና የኢኮኖሚ ቀውስ ጠባሳው እስካሁን ድረስ አልሻረም:: ለደረሰው ጉዳትና ታሪካዊ በደልም ተመጣጣኝ መልስ የሚሰጥና ከወገኖቻችን ጎን የሚቆም የሀገርና የህዝብ ፍቅር ያለው መንግስትም አልተገኘም:: ይልቁንም ከኛ የበለጠ እውቀትና ዓቅም የሌላቸው ዓረቦች ባዶ ሀገር ስላገኟት ደማችንን ብቻ ሳይሆን አንጡራ ሀብታችንም ጭምር እየጋጡና ሕብረተሰባችንንም ከሚኖርበት መሬት እያፈናቀሉ ለስደት የሚዳርጉት መሆናቸውም ጭምር ነው:: ሰሞኑን አይሲሲ የተባለው የአውሬ መንጋ በውድ ወንድሞቻችን ላይ የፈፀመው አስደንጋጭና አስነዋሪ ድርጊት እንቅልፍ የሚነሳና ልብን የሚያደማ አረሜናዊ ተግባር ነው::

በዚሁ ፈታኝ፣ አስቸጋሪና አስደማሚ በሆነበት አጋጣሚም

  1. ኢ-ሰብኣዊ በሆነ ተግባር ሰለባ ለሆኑት ወገኖቻችን ሁሉ ጥልቅ ሀዘን እየተሰማን ለሁሉም ቤተሰቦቻቸውና ለመላ የኢትዮ}ያ ህዝብ መፅናናትን እንመኛለን:: ለሞት ፅዋ የተዳረጉት ሰማእታቱንም ታሪካቸው ህያው ሆኖ በምድር ላይ ይኖራልና ነብሳቸውን በመንገስተ ሰማይ ያኑርልን::
  1. በሀገር ውስጥና በስደት ዓለም የምትገኙ ወገኖቻችን ሁሉ በዚሁ አሳዛኝ ክስተት ምክንያት ምን ያህል ልባችሁ እንደ ተሸበረ እኛም ይሰማናል:: ይህ በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው አስፈሪና አሰቃቂ በደል የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ አይደለም:: ነገም ከዚህ በባሰ መልኩ በእያንዳንዳችን ሊደርስ የሚችል ችግር ነው:: በመሆኑም መፍትሄው አንድና አንድ ነው:: እሱም ሀዘናችንን ዋጥ አድርገን ይህ የሰማእታቱን ጥሪ ለኛ መተባበርና እብረን ስለነገ ህልውናችንን ማሰብ እንድንጀምር አዲስ ምዕራፍ ለመክፈት ንስሓ የምንገባበት ጊዜ ነው::
  1. እኛን በሀይማኖት፣ በዘር፣ በቋንቋና በቦታ ከፋፍለውና እርስ በራሳችን አናቁረው ዘላለም ለመግዛት የሚፈልጉ አምባ ገነኖችም የችግሮቻችንን መንሲኤ ናቸው እንጂ በፍፁም የመፍትሄ አካል ሊሆኑ አይችሉም:: የተፈጠረውን አሳዛኝ ሁኔታም ህዝቡን የማስፈራሪያ፣ የማናቆሪያና የማለያያ ፕሮፓጋንዳ አድርገው ለመጠቀም ወደሗላ እንደማይሉ እሙን ነው:: ስለሆነም ሳይጨልም አይነጋምና የተከሰተው መጥፎ ሁኔታ አንገታችንን የሚያስደፋንና የሚስደነግጠን ሳይሆን ቀፎው እንደተነካ ንብ ከእንቅልፋችን የሚቀሰቅሰን፣ የሚለያየን ሳይሆን የበለጠ የሚያስተሳስረን፣ የሚያናቁረን ሳይሆን የበለጠ የሚያስተቃቅፈንና የሚያፋቅረን መሆኑና በተለይም ከነሱ በፊት ቀድመንና በልጠን በመገኘት የቀውጥ ቀን ለጆች መሆናችንን በተግባር ማሳየት ይኖርብናል:: ኢትዮ}ያዊ ነኝ ማለቱ መገለጫው ይኸው ነውና::
  1. ሰሞኑን የተከሰተው አስደንጋጭ ሁኔታ አላማው ኢትዮያውያንን ለማዋረድ፣ ለማሳፈርና ማንነታችንን ለማንቋሸሽ ሲባል በህዝባችንና በሀገራችን ላይ የተቃጣ የስነ ልቦና ጦርነት መሆኑን እሙን ነው:: ይህም በሕብረተሰባችን ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ቀላል አይደለም:: ሰለሆነም በሀገር ውስጥም ሆነ በዲያስፓራ በመንቀሳቀስ ላይ የምትገኙ የፓለቲካ ድርጅቶች፣ የሀይማኖት ተቋማትና አባቶች፣ የሲቢክ ማሕበራትና ሰብኣዊ መብት ተሟጓቾች ድርጅቶች፣ ምሁራኖች፣ አርቲስቶች፣ ወጣቶች፣ አክቲቪስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ የሚዲያ አውታሮችና ሌሎች ዜጎች በሙሉ ጨዋነት፣ ሃላፊነትና ጥበብ በተሞላበት አኳሃን ህዝቡን ለጋራ ችግሩ በጋራ ለመቆም ይችል ዘንድ ለማስተባበር የምትፈተኑበት ጊዜው አሁን ነው::

የጋራ ችግራችንን በጋራ ለመፍታት ተባብረን እንቁም

ኢትዮ}ያ ሀገራችን በልጆችዋ ተከብራ ለዘላለም ትኑር

Bega2260@comcast.net

The post ባለቤት ያጣ ትውልድ እንደ በግ ሲታረድ – በዲያስፓራ የዓረና ትግራይ ድጋፍ ከሚቴ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ appeared first on Zehabesha Amharic.


 ከጩኸት ወደ ተግባር የሚነገድበት የስደት ማእበል ትውልድ ከየት መጣ? ለማቆም እንረባረብ።

$
0
0

አክሎግ ቢራራ (ዶር)

ከአክሎግ ቢራራ (ዶ/ር

ከአክሎግ ቢራራ (ዶ/ር

እኛ ኢትዮጵያዊያን ከፋሽስቱ የጣሊያን ወረራ ወዲህ እንደዚህ ዓመት ተዋርደን አናውቅም። ውርደቱ ተከታታይና የማያቆም ለመሆኑ ምክንያቶቹ ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጭ ግንባርን (ህወሓት) ብሎ ከሚጠራው የጎሳዎች የበላይ ገዢ ፓርቲ ብቻ ሳይሆን እኛም ጭምር ነን። የሊቢያ ሽብርተኞች የኢትዮጵያን ወጣት ክርስቲያኖች፤ በኃይማኖታቸውና በማንነታቸው ለይተው “የእስልምና ኃይማኖት በእናንተ ኃይማኖት አማካይነት ደም ማፍሰስ ርካሽ አይደለም”(“Muslim blood that was shedunder the hands of your religion is not cheap”) ብለው ወገኖቻችንን ሲያርዷቸውና በጥይት ሲገድሏቸው ያየ ኢትዮጵያዊና ማንም በሰው ህይወት ክቡርነት የሚያምን ግለሰብ ሁሉ ቪዲወውን አይቶ እንቅልፍ ለመተኛትና በሰላም ለመኖር አይችልም። ህሊናውን ለመመራመር ይገደዳል። ይኼ ብሄር፤ ብሄረሰብ ሳይለይ፤ በንፁህ ኢትዮጵያዊያን ላይ [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

 

 

The post  ከጩኸት ወደ ተግባር የሚነገድበት የስደት ማእበል ትውልድ ከየት መጣ? ለማቆም እንረባረብ። appeared first on Zehabesha Amharic.

የዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ የሴቶች ድርጅት አጭር መግለጫ

$
0
0

ላለፉት ሃያ አራት ዓመታት ያለ ኢትዮጵያዊ መንግስት የኖረው ሕዝባችን፣ በወያኔ/ የትግሬ ነፃ አውጭ ግንባር ሁለንተናዊ ጥቃት፣ሞት እና ስደት ሲፈራረቁበት ኖሮአል። በአገሩ የመኖር ተስፋ በማጣቱ ፣ሰብዓዊ መብቱ ተጥሶ በውርደት እንዲኖር በመገደዱ የተነሳ ወጣቱ ትውልድ ስደትን እንደ አማራጭ እንዲወስድ በረቀቀ መንገድ ተገዷል። ሰሞኑን በኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ላይ በሳውዲ አረቢያ፣ በየመን ፤በደቡብ አፍሪካና በሊቢያ በተፈጸመው ኢሰብዓዊ ተጋባርና አሰቃቂ ግድያ ጥልቅና ከባድ ሃዘን ተሰምቶናል አስቆጥቶናልም።Ethiopian-Womens-Organization

የዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ የሴቶች ድርጅት የወገኖቻችን የሰማዕታት ደም በከንቱ ፈሶ የማይቀር መሆኑን እያረጋገጥን የበለጠ ተጠናክረን ለስደትና ለሰቆቃ የዳረገንን የወያኔ ስርዓትን በቆራጥነት የምናስወግድበት ወሳኝ ወቅት ላይ ደርሰናል በለን እናምናለን። በኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ላይ የመከራ እጁን ያነሳ ሁሉ ተገቢውን ዋጋውን እንደሚያገኝ ጥርጥር የለንም። በቅድሚያ ግን ለዚህ አስከፊ ችግር እና ሰቆቃ የዳረገን ፀረ ኢትዮጵያ የሆነው ወያኔ የትግሬ ነፃ አውጭ ግንባር በመሆኑ የችግሩን ምንጭ ማድረቅና መንስዔውን አሁኑኑ ማስወገድ ሰብዓዊ፣ ኢትዮጵያዊና ታሪካዊ ግዴታችን ነው። ይህ ካልሆነ ግን ኢትዮጵያውያን በአገር ውስጥም ይሁን በዓለም ዙሪያ ለከፍተኛ መከራና ችግር፣ ለወራሪዎች ኢላማ፣ የእልቂትና የሞት አውድማ የመሆን አደጋ ከፊታችን የሚጠብቀን መሆኑን ከወዲሁ መገንዘብ ይኖርብናል።

ስለዚህም ዛሬ ለተሰዉት ወገኖቻችን ማዘን ብቻ ሳይሆን፣ ዘላለማዊ ሕይወታቸው በአምላካቸው ጎን በመሆኑ ተጽናንተን ፣የፈሰሰው ደማቸው ለኢትዮጵያ ትንሳኤ ኃይልና ጉልበት እንዲሆን የሚያስፈልገውን ሁሉ ማድረግ ይጠበቅብናል። ክብራችንና ነጻነታችን ያለው በእኛ በኢትዮጵያውያን እጅ ነው፤ ከሀዘንና ከውግዘት መገለጫ ባሻገር ቆርጠን በመነሳት እውን ልናደርገው ይገባል። ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ የሴቶች ድርጅት በአገርም ውስጥ ሆነ በውጭ አገር የሚደርሰው በደልና የሚፈሰው የወገኖቻችንን ደም ከንቱ ሆኖ እንዳይቀር በተባበረ ኢትዮጵያዊ የነጻነት መንፈስ እንነሳ ዘንድ፣ ዛሬ ኢትዮጵያውያን ያለንበትን ተጨባጭ ሁኔታና ስሜትን የሚገልጸው የክላውድ ማኬ ታሪካዊ ግጥምን በማስታወስ ወገናዊ ጥሪ እናቀርባለን።

If We Must Die
Claude McKay, 1889 – 1948

If we must die—let it not be like hogs
Hunted and penned in an inglorious spot,
While round us bark the mad and hungry dogs,
Making their mock at our accursed lot.
If we must die—oh, let us nobly die,
So that our precious blood may not be shed
In vain; then even the monsters we defy
Shall be constrained to honor us though dead!
Oh, Kinsmen! We must meet the common foe;
Though far outnumbered, let us show us brave,
And for their thousand blows deal one deathblow!
What though before us lies the open grave?
Like men we’ll face the murderous, cowardly pack,
Pressed to the wall, dying, but fighting back!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ የሴቶች ድርጅት
ሚያዚያ፣ 2007

The post የዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ የሴቶች ድርጅት አጭር መግለጫ appeared first on Zehabesha Amharic.

“የችግሩ መሰረታዊ ምንጭና መፍትሔው ፓለቲካዊ ነው’!! አቶ ኤርምያስ ለገሰ

$
0
0

daniel ermiasሰሞኑን በኢትዬጲያውያን ላይ የመከራ ዶፍ እየዘነበ ነው። ይህ የድቅድቅ ጨለማ ናዳ ባስከተለው አደጋ የተፈጠረው ቁጭትና መብከንከን ከቃላት በላይ ሆኗል። በኢትዬጲያውያን ዘንድ ከዚህ ውጭ የመተከዣ አጀንዳ ያለ አይመስልም። እንባ እንደ ጐርፍ እየወረደ ነው። የእናቶቻችን ደረት በእሳት የተለበለበ እስኪመስል ድረስ እየተደለቀ ነው። ወጣቶቻችን ከአረመኔዎች ጋር ግብግብ እየገጠሙ ነው። በመንገድ፣ በትራንስፓርት፣ በምግብ ቤት፣ በስራና በተለያየ አጋጣሚ የምናገኛቸው የባእድ አገር ሰዎች ሳይቀር የሀዘናችን ተካፋዬች መሆናቸውን እየነገሩን ነው። ነግረውን ብቻ አያቆሙም ። አያይዘው ፣
“ችግሩ ለምን እናንተ ኢትዬጲያውያን ላይ ባሰ?፣ ሀገራችሁን ትታችሁ ስደትን ለምን እንደ አማራጭ ወሰዳችሁ? ለምን እንደ ጨው ዘር ትበተናላችሁ?፣ ሰብሳቢ የላችሁም ወይ? ” የሚል ጥያቄ ያስከትላሉ። የሚገርመው ነገር እንደዚ አይነት ጥያቄ በግለሰብ ደረጃ ብቻ ሳይሆን እንደተቋምም እየቀረበ ነው። ለዚህ አባባል አብነት የሚሆነኝ ባለፈው አርብ አርቲስት ታማኝ በየነ ያጫወተኝ ወግ ነው። ከእሱ ጋር በፍሎሪዳ ግዛት በነበረን ቆይታ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ኮሚሽን / ዩኤን ኤች ሲአር / ጋር እሱና የስራ ባልደረቦቹ በነበራቸው ስብሰባ ያነሱለትን ጥያቄ አንስቶ ነበር ውይይታችን የተጀመረው። ዩኤን ኤች ሲአሮች እንዲህ በማለት ነበር የጠየቁት፣
” እናንተ ኢትዬጲያውያን ሀገራችሁን ጥላችሁ በመሰደድ ተወዳዳሪ የሌላችሁ ሆናችኃል። ሌላው ቀርቶ በኢኮኖሚ አቅሟ ከእናንተ በምንም የማትሻለዋና የተንኮታኮተች ( የደቀቀች) ሀገር ወደ ሆነችው የመን እንዴት ትሰደዳላችሁ? ”
ይህ መሰረታዊ ጥያቄ ነው።እያንዳንዱ ኢትዬጲያዊ ከጊዜያዊ ዋይ ዋይታ ተቆጥቦ ከእኛ የማትሻለውን “የመን” አማትረን የምንመለከትበት ባይነኩላር ለምን እንዳስገጠምን መነጋገር ይኖርብናል። ከፊታችን እየመጣብን ያለው አደጋ ክብደትና አስፈሪነት በግልጵ አውጥተነው ችግሩን መነጋገር ያስፈልጋል።ይህን ማድረግ ካልቻልን ከራሳችን በላይ የምናስቀድማት ” ኢትዬጲያ ሀገራችን” የመኖርና ያለመኖር የህልውና አደጋ ይጋረጥባታል። ርግጡን እንነጋገር ከተባለ አሸዋ ላይ እንደተገነባ ቤት እየፈረስን ነው። የኢትዬጲያ ህዝቦች ላይ የተጠመደ ፈንጂ ለመፈንዳት ጊዜውን እየጠበቀ መሆኑ እየታየ ነው።
ቢያድለን ኖሮ ይህን አጀንዳ መክፈት የነበረበት መንግስት ነበር። ለጵድቅ ሳይሆን ከመንግስት ዋነኛ ሀላፊነቶች አንዱ ዜጐቹን ከውጭ ጥቃት የመከላከልና የህዝቡን ደህንነት የመጠበቅ ግዴታ የሚጣልበት በመሆኑ ። ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የመንግስትን ትርጉም እንደሚከተለው ገልፀውታል፣
“መንግስት ማለት የአንድን ህዝብ መሰረታዊ አቋሞች ፣ አንድነትና ነጳነት ከውጭ ጠላት የሚከላከል፣ የሕዝቡን ደህንነት ፣ እድገትና መሻሻል የሚመራ ፣ ሕዝቡ ከውስጥ እርስ በእርሱ ያለውን ግንኙነት ፣ መብትና ግዴታ በሕግና በስርአት እየወሰነ የስልጣን ባለአደራ ሆኖ የሚያስተዳድር ድርጅት ነው” በማለት ። ” መንግስታችን!” ፕሮፌሰሩ ባስቀመጡት ሁሉም መስፈርት በዜሮ ተባዝቷል። ይህም የውርደታችን ምንጭ ሆኗል። የባእዳን ማላገጫና አፍ መፍቻ ሆነናል።
ትላንት የውጭ ዜጐችን በስብሰባ፣ በትምህርት… ወዘተ ባገኘን ቁጥር ” ሉሲን ታውቃታለህ?፣ አስራ ሶስት ወር ሙሉ የፀሀይ ብርሀን ፀጋ እንዳለን ታውቃለህ?፣ ከአፍሪካ ሀገሮች በቀኝ ግዛት ያልተያዝነው እኛ እንደሆንን ይገባሀል? ” በማለት ደረታችንን ነፍተን እንናገር ነበር። ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ ይህን ማስታወሻ ስጵፍ አንድ ሁልጊዜም የማልረሳው ታሪክ አስታወሰኝ። ታሪኩ እንዲህ ነበር፣
በ1993 አ•ም• በአዲሳአባ ምክርቤት አዳራሽ በኢህአዴግ / ህውሀት የውጭ ጉዳይ ፓሊሲ ላይ ውይይት እያደረግን ነበር። የእለቱ ውይይት በፓሊሲው መግቢያ ላይ ባለው ” ብሔራዊ ውርደት” በሚለው ርእስ ላይ ነበር። በጉዳዩ ላይ አስተያየት ለመስጠት እጁን ያነሳው በወቅቱ የኮተቤ መምህራን ኮሌጅ ፕሬዝዳንት የነበረው ዶክተር ዘሪሁን ነበር። በአንድ የውጭ ኮንፍረንስ ላይ ጥናታዊ ጵሁፍ ሊያቀርብ ያጋጠመውን ነበር የነገረን። ዶክተር ዘሪሁን እንደ መንደርደሪያ ” ሉሲ፣ አስራ ሶስት ወር፣ በኮለኒ ያልተያዘች…ወዘተ” እያለ ሲደሰኩር የአንድ አፍሪካዊ እጅ ይቀሰራል። አፍሪካዊው ፍቃድ ሳይጠይቅ ” ዶክተር ለምን ጨምረህ መዝገበ ቃላት “ቸነፈር” የሚለውን ሲያብራራ ኢትዬጲያን እንደ ምሳሌ ማንሳቱን አትነግረንም?፣ …ለምን ሀገራችሁ የሟሸሸ መንግስታት በመሆኗ እንደ ሀገር መቀጠል እንዳቃታችሁ አትነግረንም?፣… ለምን በዘርና በጐሳ ተከፋፍላችሁ እንደምትኖሩ አትነግረንም?…ለምን ህዳጣን ብዙሀኑን እየገዙ መሆኑን አትነግረንም… ወዘተ ” በማለት በጥያቄ ያፋጥጠዋል። ኬሚስቱ ዶክተር ዘሪሁን በወቅቱ የሚመልሰው መልስ አልነበረውም። ጥያቄው አናሊቲካል ወይም ባዬ-ኬምስትሪ አልነበረምና!!
ዛሬም ይህ ኢትዬጲያ መሬት ላይ ያለ ሀቅ አልተቀየረም። እየባሰበት ሄደ እንጂ!…
በሀገራችን ጥቂቶች የአውሮፓና የአረብ ቅምጥል የሚኖረውን ኑሮ እየኖሩ፣ ብዙሀን በችጋር እየተገረፋ ነው።… በሀገራችን ጥቂቶች ልጆቻቸውን በአሜሪካን ሀገር በሚገኙ እጅግ ውድ ዩንቨርስቲዎች በዶላር እያስተማሩ ( የአራት ጀነራል ልጆች በጆርጅ ታወን ዩንቨርስቲ ያስተምራሉ)፣ ብዙሀን ልጁን የሚያበላው አጥቶ ከትምህርት ቤት ያስቀራል።…ጥቂቶች ባል ሜጀር ጀነራል፣ ሚስት ኮረኔል፣ ልጅ ፓይለት የመሆን እድል ይመቻችለታል፣ ብዙሀኑ “ድንጋይ ማነጠፍ ” ለመስራት አሊያም ” አፍራሽ ግብረሀይል” በቀበሌ ለመቀጠር ቦታ የለንም ይባላል።…በሀገራችን ጥቂቶች የለውጥ ውቅያኖስ ገብተው የሀብት ጋራ እንዲቆናጠጡ ይደረጋል፣ ብዙሀኑ በአፍአዊ ለውጥና ከንቱ ተስፋ እንዲሞሉ ይደረጋል። …ጥቂቶች የህሊና እምብርት ሳይበጅላቸው የሀገር ሀብት ወደ ውጭ ያወጣሉ ( በዚህ አመት ከአፍሪካ ተሰርቆ ከወጣው ቢሊዬን ዶላር ውስጥ 28•5% ከኢትዬጲያ መሆኑን ልብ ይሏል)፣ ብዙሀን በአፍሪካ ጫካ የአውሬ ራት ይሆናሉ…በሰሀራ በረሀ እንደ ሎጥ ሚስት ደርቀው ይቀራሉ… በአረብ ሀገራት እንዳበደ ውሻ ይክለፈለፋሉ ( የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል እንደወረደ!)…ጐማ ተጠቅልሎባቸው በእሳት ይጋያሉ…እንደ ዶሮ አንገታቸው ተቀንጥሶ ይጣላሉ።
ወደድንም ጠላንም የዚህ ሁሉ አቢይ መንስኤ ፓለቲካዊ ነው። የፓለቲካው መበላሸት የፈጠረው ችግር! የውስጣዊ አድልዎ ፓሊሲ የፈጠረው ችግር !…እውነት እንነጋገር ከተባለ በአድሎዋዊው ፓሊሲ ምክንያት እኩል የመማር፣ የመስራት፣ መሰረታዊ አገልግሎቶች የማግኘት እድል የለም። የፓለቲካው መበላሸት የህግ ልእልና እንዳይሰፍን አድርጓል። የህግ ልእልና ባለመስፈኑ ምክንያት ደግሞ ሀሳብን በነጳነት የመግለጵ፣ የመደራጀትና በሰላም ወጥቶ የመግባት መሰረታዊ መብት ዝግ ሆኗል። የህግ የበላይነት ባለመኖሩ ሁሉም የሀይማኖት ተቋማት በጣልቃ ገብነት እየታመሱ ይገኛሉ። በዚህም ሳይወሰን የእምነት ተቋማቱ በካድሬ ተጵእኖ በመውደቃቸው ምክንያት የእምነት ነጳነት ከስም የማያልፍ ሆኗል።
ከውስጣዊው የአድሎ ፓሊሲ ባልተናነሰ የውጭ ፓሊሲያችንም “መርህ አልባ” መሆን እና ” ጠላት ሳትፈጥር አትኑር! ” የሚለው የመለስ አስተምህሮ ለችግራችን መባባስ አስተዋጵኦ አበርክቷል። በሱማሊያ የተወሰደው የጣልቃ ገብነት እርምጃ የሳጥናኤል ጭንቅላት የተገጠመላቸው የሰው ዘር ባልሆኑት አይሲሶች ጥርስ እንዳስገባን የአደባባይ ሚስጥር ነው። በህዳር 21 ቀን 1999 አ•ም• ወደ ሱማሊያ ስንገባ አቶ መለስ ፣” ወቅታዊና ተጨባጭ የሉአላዊነት አደጋ ገጥሞናል። በኢትዬጲያ ላይ የጅሀድ ጦርነት ታውጇል ። ይህን ወቅታዊና ተጨባጭ አደጋ በአጭር ጊዜ ቀልብሰን ወደ ልማታችን እንመለሳለን” የሚል ነጋሪት በፓርላማ ጐስሞ ነበር። “ቀስ ብለን እናጢነው”፣ ” በኃላ ማጠፊያው እንዳያጥረን” ” የራሷ አሮባት የሌላውን ታማስላለች እንዳይሆንብን” እያሉ ተማጵእኖ ያሰሙትን አንጋፋ ፓለቲከኞች ( ዶክተር በየነ፣ ዶክተር መራራ፣ አቶ ቡልቻ…) ” የኢትዬጲያን ብሄራዊ ጥቅም አሳልፈው የሰጡ ከሀዲዎች፣ የሻእቢያ ተላላኪዎች” የሚል መልእክት ቀርፀን አብጠልጥለናል። ሰፋፊ መድረኮች ከፍተን ከፍ ዝቅ አድርገናል። እውነታው ግን የሱማሊያ ችግር እንኳን በአጭር ጊዜ ሊፈታ የኢትዬጲያ ወታደሮች ሱማሊያን ለቀው ሳይወጡ አስርተ አመት ሊደፍኑ አንድ አመት ብቻ ቀርቶአል። ውጤቱም ወንድሞቻችን በሰው በላ የዲያብሎስ መልእክተኛ በሆኑ አይሲሶች አንገታቸው መቀላት ሆኗል። የራሳችን አሮ የሌላውን እያማሰልን ነው!!

The post “የችግሩ መሰረታዊ ምንጭና መፍትሔው ፓለቲካዊ ነው’!! አቶ ኤርምያስ ለገሰ appeared first on Zehabesha Amharic.

የምዕራብ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪ ድብደባ ተፈፀመበት

$
0
0

11162511_701415159984145_6213321057327874841_nየሰማያዊ ፓርቲ የምዕራብ ጎጃም ዞን አስተባባሪ የሆነው አቶ አዲሱ ጌታነህ በትናንትናው ዕለት በደህንነቶች ድብደባ እንደተፈፀመበት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡ መንግስት አይ ኤስ በኢትዮጵያውያን ላይ የወሰደውን እርምጃ ለመቃወም በጠራው ሰልፍ የባህርዳር ከተማ አስተዳደርና ጸጥታ ኃላፊ አቶ አጃናው ‹‹በሰልፉ ጉዳይ መነጋገር አለብን›› ብለውት እንደነበር የገለጸው አቶ አዲሱ ‹‹ሰልፉ ላይ በግለሰብ ደረጃ እንጅ እንደ ፓርቲ ስለማንገኝ የምንነጋገረው ነገር የለም›› የሚል መልስ እንደሰጠ ገልጾአል፡፡

ከሰልፉ ቀደም ብሎ በጠዋት ወደ ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ሲያቀና ቢሮው በፖሊስ ተከቦ እንዳገኘው የገለጸው አቶ አዲሱ እሱና ሌሎች የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ሰልፉ ላይ በተሳተፉበት ወቅትም ደህንነቶች እየተከታተሉ ፎቶ ሲያነሷቸው እንደዋሉ ገልጾአል፡፡ ከሰልፉ መልስ ወደ ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ያመራው አቶ አዲሱ ከቀኑ 11 ሰዓት አካባቢ ከቢሮ ወጥቶ ወደ ቤት በሚሄድበት ወቅት በደህንነት ድብደባ እንደደረሰበት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
በደህንነቶች ድብደባ የተፈፀመበት አቶ አዲሱ ‹‹ኢህአዴግ በሀሰብ መብለጥ ሲያቅተው የነፃነት ትግሉን በኃይል ለማስቆም እየጣረ ነው፡፡ ይህ እርምጃ ትግሉን ይበልጡን የሚያጠናክረው ይሆናል እንጅ ወደኋላ የምንልበት አጋጣሚ አይኖርም›› ብሏል፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia

The post የምዕራብ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪ ድብደባ ተፈፀመበት appeared first on Zehabesha Amharic.

ሕወሓት የሚያስተዳድረው መንግስት በአ.አ ጨርቆስ አካባቢ በርካታ ወጣቶችን አፍሶ ወዳልታወቀ ሥፍራ ወሰደ

$
0
0

cherkos
(ዘ-ሐበሻ) አይሲኤል በኢትዮጵያውያኑ የፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ በመቃወም ሰልፍ የወጡት የአዲስ አበባ ሰዎች መካከል በተለይ የጨርቆስ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ወጣቶች ዛሬ በጠዋቱ ሲታፈሱ መዋላቸውን ለዘ-ሐበሻ ከአዲስ አበባ የደረሰው መረጃ ጠቆመ::

በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የለውጥ መነሳሳት ስሜትን በሰሞኑ ሰላማዊ ሰልፎች ላይ የተመለከተው ሕወሓት መራሹ መንግስት በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ይገኛል ያሉት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ቀጣዩን የውሸት ምርጫ ካለምንም ኮሽታ ለማሳለፍ ሲል ወጣቶችን በማሸበር ላይ ይገኛል ብለዋል::

ሕወሓት የሚያስተዳድረው መንግስት ዛሬ በጨርቆስ አካባቢ ከአንድ መቶ የማያንሱ ወጣቶችን አፍሶ የወሰደ ሲሆን የት እንደደረሱ ለማረጋገጥ ያደረግነው ጥረት አልተሳካም::

The post ሕወሓት የሚያስተዳድረው መንግስት በአ.አ ጨርቆስ አካባቢ በርካታ ወጣቶችን አፍሶ ወዳልታወቀ ሥፍራ ወሰደ appeared first on Zehabesha Amharic.

ሕገ ወጥ ጎብኚ እንጅ ሕገ ወጥ ስደተኛ የለም!

$
0
0

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ስደት ሕዝባችንን ከቀየው እያፈናቀለ በአራቱም መዓዝናተ ዓለም ማንከራተት ማንቀዋለል ማንገላታት ከጀመረ አራት ዐሥርት ዓመታት ሞላ፡፡ በደርግ ጊዜ ከተሰደዱት በዘመነ ወያኔ የተሰደዱት እኅት ወንድሞቻችን እናት አባቶቻችን እጅግ ይበዛሉ፡፡ ስደተኛ ወገኖቻችን በየተሰደዱበት ሀገር እንደሰው ታይተው የሰውነት ክብር የተነፈጋቸውና ብሔራዊ ክብራችን የወደቀው የተደፈረው የተዋረደው በዘመነ ወያኔ ነው፡፡ የሚገርመው ወያኔም ያው ቢሆንም ጨፍጫፊ የምንለው ደርግ “የዜጎች መዋረድ መደፈር የሀገር መዋረድ መደፈር ወይም ብሔራዊ ውርደት ነው” የሚል እንደ መንግሥት ከአንድ መንግሥት የሚጠበቅ ጠንካራ አቋም ስለነበረው ሌላው ቀርቶ ሊገላቸው የሚፈልጋቸው ተቃዋሚዎቹ አምልጠው በስደት ባሉባቸው የጎረቤት ሀገራት ችግርና እንግልት ሲገጥማቸው ለያሉበት ሀገር መንግሥት ከባድ ማስጠንቀቂያ በመስጠት መብቶቻቸው እንዲጠበቅ ያደርግ ነበር፡፡ በዘመነ ወያኔ ግን የሀገራችንና የዜጎች ክብርና ሞገስ እጅግ በሚያስደነግጥ እጅግ በሚያሳዝን እጅግ በሚያሳፍር ደረጃ በመውደቁ የሀገራችንና የዜጎቿ ክብርና ሞገስ የትም ቦታ በማንም ምናምንቴ ሁሉ የሚደፈር የሚረገጥ መጫወቻ መቀለጃ ለመሆን በቅቷል፡፡
video-migrant-boat-capsizes-near-italy-leaving-200-people-in-the-sea
ዜጎች በየተሰደዱበት ሀገራት ሀገርና መንግሥት እንደሌላቸው ኢሰብአዊ በደሎች ሲፈጸምባቸው ግዴታውን አውቆ አለሁ የሚላቸውና መብቶቻቸውን የሚያስከብርላቸው አንድም ዓይነት አካል አልባ ሆነዋል፡፡ በዘመነ ወያኔ ሀገራችንና ዜጎች እንዲህ ዓይነት ችግር ሊጋፈጡ ግድ ያለበት ምክንያት የወያኔ አገዛዝ የመንግሥት ቅርጽና አቋም ይዞ መንግሥት የሚጠበቅበትን ኃላፊነቶችና ግዴታዎች ለመወጣት የሚያስችል ፖለቲካዊ (እምነተ አሥተዳደራዊ)፣ ሞራላዊ (ቅስማዊ)፣ ግብረገባዊ አቅም ብቃት ፍላጎትና ፈቃደኝነት አልባ በመሆኑ ነው፡፡ ይህ ሽባና ነውረኛ አገዛዝ ዜጎች በየተሰደዱበት ሀገራት ችግር በገጠማቸው ቁጥር ደርሶላቸው የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ላለመወጣቱ የሚያቀርበው ምክንያትና ሽፋን “ሕገ ወጥ ስደተኞች ናቸው” የሚል ነው፡፡ ሕገ ወጥ ስደተኞች ስለሆኑም እነሱን ልረዳ የምችልበት ሕጋዊ አኪያሔድ የለኝም ይላል፡፡ ይህ ምክንያት በወያኔ አገዛዝ የተፈጠረ አስቀድሞ በነበረው ያልነበረ መሆኑን ልብ በሉ፡፡ ወያኔ ይሄንን የሚልበት የራሱ የሆነ ምክንያት አለው ወደ ኋላ ዕናየዋለን፡፡ ለነገሩ ወያኔ እንዲህ ይበል እንጅ ወገኖቻችን በየተሰደዱበት ሀገራት ኢሰብአዊ ግፍና በደል እየደረሰባቸው ካሉ ወገኖቻችን ከፊሎቹ በሚገባ ሕጋዊ የመኖሪያና የሥራ ፈቃዶች ያሏቸው ናቸው፡፡ ይሄም ቢሆን ግን ለሚያቀርቧቸው የእርዳታና የድረሱልኝ ጥሪ የአገዛዙ ኤምባሲ (የመንግሥት እንደራሴ) እና የቆንሲላ (የመንግሥት ጉዳይ አማካሪ) ጽ/ቤቶች አንድም ዓይነት የሚጠበቅባቸውን አዎንታዊ ምላሽ የሚሰጡ አይደሉም፡፡ አገዛዙ እንዲህ ዓይነቱን ሴራ በዜጎች ላይ የሚፈጽምበት ምክንያት 1. አገዛዙ በሙሉ ትኩረቱ የሙሉ ጊዜ ሥራው አድርጎ የያዘው የሀገርና የዜጎችን ክብር በመሸጥ ጭምር ሁሉንም አማራጮች በመጠቀም ጥቅሙን ማስጠበቅ ህልውናውን ማራዘም ስለሆነ፡፡ 2. ከቡድኑ ጥቅምና ቆሜላቸዋለሁ ከሚላቸው ወገኖቹ በስተቀር የሌሎችን ኢትዮጵያዊያን ወገኖችን ደኅንነት ጉዳይ ከመጤፍ የሚቆጥር ባለመሆኑ 3. አገዛዙ በሌሎች መንግሥታት ዘንድ እንደ አንድ መንግሥት የሚታፈር የሚከበር ባለመሆኑ ክብርና ሞገሥ አልባ በመሆኑ ናቸው፡፡ እነኝህን ደካማ የወያኔ አስተሳሰቦች ደግሞ ሁሉም በየትም ቦታ ስለሚታወቅ “ባለቤቱን ቃልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ” እንደሚባለው ሁሉ የወያኔን ልብና አቅም ጠልቀው የሚያውቁት ባዕዳን በወገኖቻችን ነፍስ እንዳሻቸው ለመጫወት ለመቀለድ ድፍረቱን አገኙ፡፡

በእነዚህ ሰንካላና የደንቆሮ ምክንያቶቹ ግዴታውን የማይወጣው ወያኔ ግዴታውን ላለመወጣት “ሕገ ወጥ ስደተኛ” የሚለውን ቃል መሸሸጊያ አድርጎታል፡፡ ከወያኔም ውጪ ከሀገር ውጪ ያሉ ዜጎቹን ደኅንነትና መብት ላለማስጠበቅ ከኃላፊነቱ ለመሸሽ ይሄንን ቃል የሚጠቅስ ሞራሉ (ቅስሙ) የላሸቀ በመንግሥት ስም ያለ አካል አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡ ለሌሎቹ መንግሥታት በየትም ሀገር ያለ ዜጋቸውን መብቶችና ደኅንነቶች ለማስጠበቅ ዜጋቸው ሆኖ ከመገኘቱ የበለጠ በቂ ምክንያት የላቸውም፡፡ እነዚህ ሀገራት ዜጎቻቸው ተሰደው በሚኖሩበት ሀገራት መብትና ደኅንነቶቻቸውን ማስጠበቅ አይደለም የመጨረሻ ከባድ የሚባል ወንጀል ሠርተውም በተገኙበት ወቅት እንኳን ቢሆን በተቻላቸው መጠን ሁሉ በወንጀሉ ከመጠየቅ ነጻ እንዲሆኑ እስከማድረግ ድረስ ከጎናቸው ይቆማሉ፡፡ ወያኔ ግን በተቃራኒ አቅጣጫ በመጓዝ የዜጎችን መብትና ደኅንነቶቻቸውን ላለማስጠበቅ ነው አንዴ ሕገ ወጥ ስደተኛ ሌላ ጊዜ ኢትዮጵያዊነታቸውን የሚያረጋግጥ ሰነድ የላቸውም እያለ ዐሥር ምክንያት እየፈጠረ ኃላፊነቱን ላለመወጣት ጥረት የሚያደርገው፡፡
ይህችን “ሕገ ወጥ ስደተኛ” የምትል ቃል ወያኔ ብቻ አይደለም የሚጠቀምባት ምዕራባዊያን ሀገራት የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራትና ሌሎቹም ጭምር እንጅ፡፡ ልዩነቱ እነሱ ቃሉን የሚጠቀሙት ለዜጎቻቸው ሳይሆን ከተለያዩ ሀገራት ወደየሀገሮቻቸው ለሚገቡት ስደተኞች ሲሆን ወያኔ ደግሞ ቃሉን የሚጠቀመው ለወገኖቻችን መሆኑ ነው፡፡ እነሱ ለስደተኞች ይህንን ቃል የሚጠቀሙበት ምክንያትም የስደተኞቹን የስደተኝነት መብት ላለማክበር ሊያደርጉት የሚጠበቅባቸውን መስተንግዶ ላለመስጠት ላለማቅረብ ግዴታና ኃላፊነታቸውን ላለመወጣት ለመሸሽ ነው፡፡

ሲጀመር ሕገወጥ ስደተኛ ማለት ምን ማለት ነው? የቃሉ አጠቃቀምስ ትክክል ነው ወይ? ብለን ስንመረምር ፍጹም የተሳሳተ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ስደተኛ ያሰደደው አንዳች አስገዳጅ ምክንያት ከሌለ በስተቀር አይሰደድም፡፡ ስደተኛ የሚሰደደው ያለበት አካባቢ ወይም ሀገር ለሕይዎቱ አደገኛ ሲሆንና ከተጋረጠበት አደጋ ሕይዎቱን ለማትረፍ ሲገደድ ነው፡፡ ስደተኛ የሚሰደደው የነፍስ ጭንቅ ሲይዘው ሲያጋጥመው ነው፡፡ ስደተኛ የሚሰደደው ጭላንጭል ተስፋ ሲያጣ ነው፡፡ ስደተኛ የሚሰደደው ምክንያቱ ፖለቲካዊ (እምነተ አሥተዳደራዊ)፣ ማኅበራዊ፣ ሃይማኖታዊ የመሳሰሉት ሊሆን ይችላል በእነዚህ ምክንያቶች አሳዳጅ ሲኖርበትና ሲያሳድደው ነው፡፡

በእነኝህ አስገዳጅ ምክንያቶች ተገፍቶ ነፍሱን ለማዳን ለማቆየት እግሩ ወዳመራው የተሰደደን የሰው ልጅ ሁሉ ሁሉም የመንግሥታቱ ድርጅት አባል ሀገራት ሁሉ የመቀበል ተቀብሎም የማስተናገድ ግዴታ እንዳለባቸው የፈረሙት ስምምነት (convention) ይደነግጋል፡፡ ስደተኛ እነኝህን ያሰደዱትን ችግሮች ሁሉ ለመከላከል ሳይችል ቀርቶ ከአቅሙ በላይ ሆነውበት አፈናቅለው ያሰድዱታል እንጅ ወዶና ፈቅዶ በራሱ ላይ እንዲመጡበት እንዲፈጠሩበት እንዲከሰቱበት አድርጎ አይሰደድም፡፡ የሰው ልጅ ተረጋግቶ አስቦ አውጥቶና አውርዶ ወዶና ፈቅዶ ከሚኖርበት ሀገር ወደ ሌላ መሔድና ማየት የሚፈልገውና ወደዚያ ሀገርም ለመግባት ፈቃድ መጠየቅ ግድ የሚሆንበት ጎብኚ ሆኖ ያችን ሀገር ለመጎብኘት ሲያስብ ነው፡፡ የመጎብኘት ፍላጎት ሰላማዊና በፍላጎት ላይ የተመሠረተ ነው ከጀርባው የሚገፋው የሚያስገድደው ሰላማዊ ያልሆነ አንዳችም አስገዳጅ ክፉ ምክንያት የለም፡፡ ስለሆነም ገብቶ ለመጎብኘት ሊጎበኘው የፈለገውን ሀገር ፈቃድ ማግኘት ይጠበቅበታል፡፡ ፈቃድ ሳያገኝ ገብቶ ከተገኘ ይህ ሰው ሕገ ወጥ ነው የሀገሪቱ ምንግሥትም የሀገሪቱን ደኅንነት አደጋ ላይ ለመጣል እንደሚያሴር ሰላይ ሊቆጥረው ሊጠረጥረው ይችላል፡፡ ስደተኛ ግን እንዲህ አይደለም ድስት የሚገነፍለው ምን ሲሆን ነው? ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት ስደተኛ የሚሰደደው በአስገዳጅና ጊዜ በማይሰጡ ምክንያቶች ነው፡፡ ተሰዳጁ የሚሰደድባቸው ሀገራት ይሄንን በአስገዳጅ ምክንያት የተሰደደን ሰው የመቀበል የማስተናገድ የሰብአዊና የሞራል (የቅስም) ግዴታ አለባቸው፡፡ ከሰብአዊነትና ከቅስም አንጻር ልናስተናግዳቸው የሚገቡ ነገሮች ሁሉ ምንም ዓይነት ቅድመ ሁኔታ አይጠየቅባቸውም፡፡ አንዳች አውሬ ሊበላው እያሳደደው የነፍስ ጭንቅ ይዞት አድኑኝ እርዱኝ እያለ ሮጦ ዘሎ እሰው ቤት የገባ ሰው “በር አላንኳኳህም ሳይፈቀድልህ ግባ ሳትባል ነው የገባኸው ስለሆነም ሕገ ወጥ ነህ” ሊባል በፍጹም አይገባም ይህ ኢሰብአዊ ኢግብረገባዊ ኢቅስማዊ ፍረጃ አባባልና አስተሳሰብ ነው፡፡ ሰውየው ላንኳኳ ግባም እስክባል ልጠብቅ ካለ መበላቱ ነውና ማንኳኳትና ግባ እስኪባል መጠበቅ አይኖርበትም፡፡ ስለሆነም የጎብኚ እንጅ የስደተኛ ሕጋዊና ሕገወጥ የሚባል ነገር የለም፡፡ ቃሉ ራሱ ኢፍትሐዊና አጥቂ ቃል ነው፡፡ ቃሉ የተፈጠረውና እየተገለገሉበትም ያለው ኃላፊነታቸውንና ግዴታቸውን ላለመወጣት በሚጥሩ መንግሥታትና አካላት ነው፡፡

ከሀገራችን በተለያየ ምክንያት ዜጎች ቀያቸውን ለቀው ይሰደዳሉ ወገኖቻችን የሚሰደዱባቸው ሀገራት ወገኖቻችንን ላለማስተናገድ የሚጠቀሙበት አንድ ሌላ ቃል አለ “የኢኮኖሚ (የችጋር) ስደተኞች” የሚል፡፡ በዘመነ ወያኔ ከሀገራችን አንድም የኢኮኖሚ (የችጋር) ብቻ ተብሎ ሊጠራ የሚችል ስደተኛ የለም፡፡ ይሄንን ማንም ሰው ሊያረጋግጥ ይችላል፡፡ ምንም እንኳን ላይ ላዩን ሲያዩት ይምሰል እንጅ ዜጎች ከገጠር እስከ ከተማ እየተሰደዱ ያሉት በፖለቲካዊ (እምነተ አሥተዳደራዊ) በሆነ ምክንያት ነው፡፡ ገበሬው ወያኔ ካልሆንክ ወደድክም ጠላህም እኛን በግድ ካልደገፍክ ምርጥ ዘር ማዳበሪያና ሌሎችንም በዜግነቱ ሊያገኛቸው የሚገባውን ጥቅሞች አታገኝም በመባሉ ለችጋር ተዳርጎ በተፈጠረበት ድህነት ልጆቹ እየተሰደዱ ባለበት ሁኔታ፤ በከተማም ወያኔ ካልሆናቹህ በስተቀር ተብሎ ዜጎች በዜግነታቸው ብቻ ሊያገኝዋቸው የሚገቡትን ከሥራ እስከ ከፍተኛ የትምህርት ዕድል ልታገኙ አትችሉም ተብሎ ደንቆሮው አገዛዝ ደንቆሮና አንባገነናዊ አቋም በመያዙ ዜጎች ለችግር በመዳረጋቸው ምክንያት ለመሰደድ በተገደዱበት ሁኔታ ወገኖቻችንን የኢኮኖሚ (የችጋር) ስደተኞች ብሎ ማለት እጅግ የተሳሳተ ፍረጃ ነው፡፡ ፍረጃው ምን ያህል ማስተዋል የጎደለውና ኢፍትሐዊ እንደሆነ ማየት ይቻላል፡፡ ምክንያቱ ባይገባኝም ሲጀመር ጀምሮ ዓለም እኛን በተመለከተ በምንም ነገር ላይ ትክክለኛ ፍርድን ሲፈርድ ታይቶ አይታወቅም፡፡ ዜጎች በኢፍትሐዊ ብየና እንደተፈረጁና እንደተንገላቱ አሉ ለወደፊቱም ይኖራሉ፡፡ ኢትዮጵያዊ ሆኖ ብቻውን የኢኮኖሚ (የችጋር) ስደተኛ የለም፡፡ ምክንያቱም ያ ያሰደደው ችጋር የተፈጠረው በወያኔ ኢፍትሐዊና አንባገነናዊ አሥተዳደር ነውና፡፡ ይሄንን ስደተኛ ወገኖቻችንን የሚቀበሉ ሀገራትም ሆኑ የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኛ ተንከባካቢ ድርጅቶች አሳምረው ያውቁታል፡፡

እነኝህ ሀገራት ወገኖቻችን በግልጽ የፖለቲካ ስደተኞች መሆነናቸው እየታወቀም የፈረሙትን የመንግሥታቱ ድርጅትን ሕግ በመጻረር ወገኖቻችንን እያነቁ ለወያኔ አሳልፈው ሲሰጡ ለበርካታ ጊዜያት ተስተውለዋል፡፡ የመንን፣ ጅቡቲን፣ ሱዳንን፣ ኬንያን ዩጋንዳን ሌሎችንም መጥቀስ ይቻላል፡፡ ከአውሮፓም ኖርዌይን በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል፡፡ ዓለም ለእኛ መቸም ፍትሐዊ ሆኖ አያውቅም ይሆናልም ብየ አልጠብቅም፡፡ የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኛ ተንከባካቢ ድርጅቶች ወገኖቻችን ተሰደው በሚገኙባቸው ሀገራት የፖለቲካ ስደተኞች መሆናቸውን እያወቀም ወያኔና ሀገሮቹ በመመሳጠር ከሚያደርሱባቸው አፈና ሊታደጋቸው አልቻለም ሞክሮም አያውቅም፡፡ አደዳው ሲያጋጥምም የመንግሥታቱን ድርጅት ሕግ የሚጥስ የሚጻረር መሆኑን በመግለጽ አደጋውን ያደረሰባቸውን የዚያን ሀገር መንግሥትና የወያኔን አገዛዝ በመወንጀል አሥተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ሲያደርግ ታይቶም ተሰምቶም አይታወቅም፡፡ የፖለቲካ ስደተኛ ወገኖቻችን በእነዚህ ሀገራት ላሉ የመንግሥታቱ ድርጅት ስደተኛ ተንከባካቢ ድርጅቶች ማመልከቻቸውን ሲያቀርቡ ከሌሎች ሀገራት ፍጹም በተለየ መልኩ ብዙ እንግልት ይደርስባቸዋል፡፡ በድርጅቱ ያሉ ሠራተኞች የወያኔ ቅጥር ሠራተኞች ነው የሚመስሉት፡፡ ወገኖቻችን ከሌላው በተለየ መልኩ አግባብነት ፍጹም የሌለው መስተንግዶና እንግልት እንዲደርስባቸው ለምን እንደሚደረግ ፍጹም ግልጽ አይደለም፡፡ በእነዚህም ምክንያቶች ወገኖቻችን ችግር ገጥሟቸው ሲሰደዱ እንግልትና ተቀባይነት የማጣት ችግርን በመፍራት ኢትዮጵያዊነታቸውን ደብቀው ኤርትራዊ ወይም ሶማሊያዊ ነኝ በማለት በስደተኝነታቸው ሊያገኙ የሚገባቸውን ጥቅም ለማግኘት ጥረት ያደርጋሉ፡፡ በቀይ ባሕርና በሜዲትራኒያን ባሕር ስደተኞች የመስጠም አደጋ ደርሶባቸው ሲያልቁ ኤርትራዊያን ወይም ሶማሊያዊያን ተብለው ከሚገለጹት ማቾች ከ70% በላይ የሚሆኑት ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ናቸው፡፡ አውሮፓ ወይም መካከለኛው ምሥራቅ የገባ ዘመድ ወዳጅ ወይም የምታውቁት ሰው ካላቹህ ምናዊ ነኝ ብለህ ገባህ? ለምን? በሉና ጠይቁት ይነግራቹሀል፡፡

ምዕራባዊያን በእኛ ስደተኞች እጅግ እንደተማረሩ በየመድረኩ በምሬት ያወራሉ፡፡ ለዚህ ስደት የዳረገንንም ችግር ከእኛ በላይ ጠንቅቀው ያውቃሉ መፍትሔውንም ጭምር፡፡ ያላቸው ምርጫ ሁለት ነው ለመሰደዳችን መንስኤ ለሆነው አንባገነናዊ አገዛዝ ምንም ዓይነት ድጋፍና እርዳታ ባለማድረግ የራሳችንን ጉዳይ እኛው እንድንፈታው ለእኛው በመተው አንባገነን አገዛዞችን ተገላግለን በይነሕዝባዊ (ዲሞክራሲያዊ) አሥተዳደር እንድንመሠርት መንገዳችን ላይ ጋሬጣ ባለመሆን መተባበር ወይም በስደተኛ ጎርፍ ለመጥለቅለቅ መፍቀድ፡፡ ምዕራባዊያን ለወያኔ የብረት ምሰሶ ድጋፍ ባይሆኑ ኖሮ እውነቴን ነው የምላቹህ ይሄንን ስልም መቶ በመቶ እርግጠኛ ሆኘ ነው 23 ዓመታት አይደለም አንድ ዓመት እንኳን የመቆየት አቅም ባልነበረው ነበር፡፡ ነገር ግን ምዕራባዊያን ፍጹም አግባብነት ፍትሐዊነት ለሌለው ለከት አልባ ርሕራሔ ቢስ ለሆነው ጥቅማቸው ወያኔን እየደጋገፉ እዚህ አድርሰውታል፡፡ በአሁኑ ዘመን ምዕራባዊያን የሞግዚት አሥተዳዳሪዎቻችን ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ መንግሥት አልባ ከሆነችና ሉዓላዊነቷን ካጣች 23 ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ በሀገራችን ያለው አሥተዳደር የሞግዚት አሥተዳደር ነው፡፡

ሰሞኑን የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ምክትል ሚንስትር ያለችውን አልሰማቹህም? ሴትዮዋ የሀገሯ መንግሥት በየዓመቱ የሚያወጣውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሀገራት የሰብአዊ መብት አያያዝ የሚተነትንበትን መግለጫ በተጻረረ መልኩ የወያኔ አገዛዝ ዲሞክራሲያዊ መሆኑንና በዚህ ዲሞክራሲያዊ መንግሥት ማንም ብረት ማንሣት አይደለም ክፉ ነገር እንኳን ይናገርና ዋ! አይማረኝ ላልምረው” ማለቷን ሰምታቹሀል፡፡ አሜሪካን ስናውቃት ለሐሳብን በነጻ የመግለጽ ዲሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብት ጠበቃ ነኝ በማለቷ እራሷን የዓለም ፖሊስ አድርጋ በመሾምም ይሄንንና ሌሎች ተጓዳኝ ዲሞክራሲያዊ (በይነ ሕዝባዊ) መብቶችን በዓለም ሀገራት ሁሉ አሰፍናለሁ ስትል ነበር የምናውቃት፡፡ ሴትዮዋ ባደረገችው ንግግር ግን “የተቃውሞ ሐሳባቹህንም እንኳን ቢሆን በአገዛዙ ላይ መግለጽ አትችሉም ጸባቹህ ከኔ ጋር ነው!” ስትል ዩ. ኤስ. አሜሪካ ቆሜለታለሁ የምትለው እሴት የውሸት መሆኑን አረጋገጠች፡፡ ለካ ያ ሁሉ በየዓመቱ ይወጣ የነበረ መግለጫ ሁኔታወችን ከዓለም ፖሊስነቷ ጋር ለማጣጣም ሲባል ለማስመሰል ይነገር የነበር ዲስኩር ኖሯል? አዎ! ያም በመሆኑ ነው በእርምጃ ሊደገፍ ያልቻለው፡፡ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ተብየው የሀገር ሉዓላዊነት ማለት ምን ማለት እንደሆነ ቢገባቸው ኖሮ ይህንን ድንበር ያለፈ የሀገርን ሉዓላዊነት ተዳፍሮ አለቅጥ በውስጥ ጉዳይ ላይ አራጊ ፈጣሪ ነኝ በሚል ስሜት ጣልቃ ተገብቶ የተነገረ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ምክትል ሚንስትር ንግግርን አጥብቀው በተቃወሙና እዛው ላይም እንዲታረም በጠየቁ ነበር፡፡ ሰውየው ግን ከዚህ ይልቅ ልባቸው ከበሮ እየደለቀ ነበር በደስታ የፈነጠዙት፡፡ የሞግዚት አሥተዳደር ቡችላ አሻንጉሊት ሉዓላዊነትን የት ያውቅና!፡፡ አሜሪካኖች “ሌላ ቀን መጥቶ ይሄ ቀን ያልፍና ያስተዛዝበናል ያ ቀን እንደገና” የሚለውን ተረት አያውቁትም ይሆን? አደራ እንዳትረሱብን በሉልኝ እባካቹህ ቅርብ የሆናቹህ ወገኖች፡፡

ትናንት ሚያዝያ 15 2007ዓ.ም. የአውሮፓ ሕብረት ሀገራት መሪዎች ከአፍሪካ የሚገቡ ስደተኞችን በተመለከተ ያደረጉትን አስቸኳይ ስብሰባ ውሳኔዎችን በማሳለፍ አጠናቀዋል፡፡ በውሳኔዎቻቸው ይሄንን ስደት ለመከላከልና ለመቆጣጠር እየተደረገ የነበረውን ጥረት በሦስት እጥፍ በማሳደግ አዘዋዋሪዎችንና ደላሎችን ለመቆጣጠር፣ ጀልባዎችን ስደተኞችን ከመጫናቸው በፊት በሄሊኮፕተር በታገዘ ወታደራዊ ኃይል ለመደምሰስ የውሳኔ ሐሳቦችን በማሳለፍ ተስማምተው ተበትነዋል፡፡ የሠለጠነው ዓለም መሪዎች ሆይ! በቃ ይህችን ታክል ነው ማሰብ የምትችሉት? ውሳኔዎቻቹህ እጅግ አሳፋሪና ዘመኑን የማይመጥን ያለውንም ችግር ለመፍታት የማይበቃ ደካማ ውሳኔ ነው፡፡ በቃ ይሄው ነው መፍትሔው? ይሄ ላለው ችግር ዘላቂ መፍትሔን ያመጣል? በችግሩ መንስኤ ላይ ማተኮር አይሻልም? ይሄንን ለማሰብ ለምንድነው የማትፈልጉት? ለእኛ ከቀያችን እየተፈናቀልን መሰደድ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የእናንተ እጅ ስላለበትና የሞራል ብቃትና ወኔ ስላጣቹህ ነው? ስለዚህም ተገደን ከቀያችን ከሀገራችን ተፈናቅለን በገፍ ወደ ሀገሮቻቹህ በምንሰደድበት ጊዜ “ሕገ ወጥ ስደተኞች” እያላቹህ እኛን የማሸማቀቅ የሞራል (የቅስም) እና የፖለቲካ መብትና ብቃት የላቹህም፡፡ ስደተኛውን ከቀየው ከገዛ ሀገሩ እየተፈናቀለ ሳይወድ እንዲሰደድ በሚያደርገው ችግርና መፍትሔው ላይ አተኩራቹህ ሳትሠሩ ስደተኛ ይቁም፣ ደላላና አዘዋዋሪ ይጥፋ፣ ጀልባዎች ይደምሰሱ ብትሉ ወደ አውሮፓ የሚሻገሩ የኢትዮጵያን (ኤርትራን ጨምሮ) ስደተኞችን ይሄንን መስመር ጨርሶ እንዳያስቡ ለማድረግ ሰሞኑን በ30 ወንድሞቻችን መታረድና መረሸን ጀርባ የእናንተ እጅ ቢኖርበትምና በቀጣይም ተጨማሪ ሌላ ተመሳሳይ ግፍ ቢፈጸምም እንኳ ስደተኛ ይቆማል ብላቹህ ከቶውንም እንዳታስቡ፡፡

እባካቹህ! እናንት የምዕራባዊያን ምንግሥታት መሪዎች ሆይ! እባካቹህ? መንግሥቶቻቹህን በየግል ብልሹ ሰብእናዎቻቹህ መስመር እንዲጓዙ እንዲቃኙ አታድርጓቸው? መንግሥት የሚባለው ተቋም እኮ ልክ እንደ ሃይማኖት ተቋም ሁሉ ለሰብአዊነት፣ ለእውነት፣ ለፍትሕ፣ ለትክክለኛነት፣ ለእኩልነት፣ ለሞራል(ለቅስም) ድንጋጌዎች ከልብ የመገዛት ግዴታ ያለበት ተቋም እኮ ነው፡፡ ግፈኛ፣ ሸረኛ፣ ቁማርተኛ፣ ሐሰተኛ ሊሆን እኮ አይገባም! እንዲህ ዓይነት ደካማ የየግል ሰብእናቹህን ሳትጥሉና የመንግሥት ባለሥልጣን ሊይዘው የሚገባውን ምስጉን ሰብእና ሳትላበሱ ወደ መንግሥቶቻቹህ እየገባቹህ በምትሠሯቸው እኩይ ኢሰብአዊና ግፈኛ ተግባሮቻቹህ እኮ እኛ ተቸገርን፣ ተሰቃየን፣ ፍዳችንን በላን ኧረ እባካቹህ ስለፈጠራቹህ! ስለ ጉልበታቹህ አምላክ ብላቹህ እዘኑልን? ተውን? መንግሥቶቻቹህ ባላቸው ታማኝነት፣ ቅንነት፣ እውነተኛነት፣ ሀቀኝነት እንደ ሃይማት ተቋም ሁሉ የሚከበሩ፣ የሚታፈሩ፣ የሚፈሩ፣ የሚፈቀሩ መሆን እኮ ነበረባቸው! አለዛማ የወንበዴ ቡድን እንጅ ምኑን መንግሥት ሆናቹህት? በእውነት የሚያፍርና የሚሰማው ሰብእና ካላቹህ ልታፍሩ እኮ ይገባል፡፡ መንግሥቶቻቹህ በምስጉት ሰብእና የተገነባ ቢሆን ኖሮ እኮ ዓለም ፍጹም ሰላማዊ በሆነች ነበር፡፡ አንደኛው ሁለተኛው አሁን ደግሞ በምታደርጉት እኩይ ሴራ በየሀገሩ የተደረጉትና የሚደረጉትም ጦርነቶች እልቂቶች ባልተፈጠሩ ነበር፣ ሰው ከቀየው እየተፈናቀለ ባልተሰደደ ነበር፣ እናንተም በስደተኛ ባልተቸገራቹህ ነበር፡፡ “ሰው የዘራውን ያንኑ ያጭዳል” ነውና የሚለው ቃሉ የዘራቹህትን ነው የምታጭዱት፡፡ የፈሰሰውና የሚፈሰው ደማችን እንዲሁ በከንቱ የሚቀር ይመስላቹሀል? በኃያሉ አምላክ ፊት ይፋረዳቹሀል! እናንተ ታርማቹህ ሰላም እንድንሆን ለማድረግ ባትፈቅዱም እረፍትና መዳን ለእኛ ከሌላ ስፍራ ይሆንልናል እናንተና የአባቶቻቹህ ቤት ግን ትጠፋላቹህ!!!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለለም ትኑር!!!

The post ሕገ ወጥ ጎብኚ እንጅ ሕገ ወጥ ስደተኛ የለም! appeared first on Zehabesha Amharic.

በአትላንታ ጆርጂያ የሻማ ማብራትና የጸሎት ሥነ ሥርዓት ተካሄደ

$
0
0

atlanta

atlanta 2

atlanta 3

atlanta 5

atlanta 6
በቅርቡ በሊቢያ የባህር ዳርቻ ፣ በግፍ የተረሸኑትንና የታረዱትን፣ እንዲሁም በደቡብ አፍሪካ፣ በየመን እና በሌሎችም የዓለማችን ክፍሎች በችግርና በስቃይ ውስጥ ያሉትን ወገኖችን ለማሰብ የተዘጋጀ የሻማ ማብራትና የጸሎት ስነ ሥርዓት፣ በአትላንታ ከተማ ተካሄደ።

በዚሁ ከስድስት መቶ የማያንስ የአትላንታ ነዋሪ በተገኘበት ስነ ሥርዓት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ፣ ከፈርስት ሂጂራ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተወካይ፣ ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን እና ከኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አትላንታ አባቶች ተገኝተው በየተራ ጸሎት በማድረግ መርሃ ግብሩን የከፈቱ ሲሆን፣ የኢትዮጵያውያን ጆቫ ዊትነስ ጉባዔ በጊዜ መጣበብ መምጣት አለመቻላቸው ተነግሯል።

በዚሁ የጸሎትና የሻማ ማብራት ስነ ሥርዓት ፣ በሁሉም አባቶች መንፈሳዊ ምክር የተሰጠ ሲሆን፣ በተለይም ሃጂ ሳፊ አላሚን ከፈርስ ሂጂራ ያቀረቡት ግጥም ታዳሚውን በእምባ ያራጨ ነበር። በእምነት አባቶቹ ምክር መካከል በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ ቋንቋዎች ግጥሞችና መጣጥፎች ቀርበዋል።

የወገኖቻችን ሞትና እስራት፣ መከራና ችግር፣ ስቃይና መቃተት የሁላችንም ስሜት እንደሆነ በተነገረበት በዚህ ዝግጅት፣ የዕምነት ተቋማት አንድ መሆንና መቀራረብ ለተቀረው ማህበረሰብ መቀራረብና አንድነት ወሳኝ በመሆኑ በአትላንታ ሁሉንም ኢትዮጵያውያን የዕምነት ተቋማት የሚያካትትና ቢያንስ በየሶስት ወሩ እየተገናኙ በጋራ በሚያገናኟቸው የማህበረሰብ ጉዳዮች ላይ የሚወያዩበት “በአትላንታ የዕምነት ተቋማት የጋራ ጉባዔ” እንዲመሰረት ሃሳብ ቀርቦ ከእምነት አባቶቹ ተቀባይነትን ሲያገኝ፣ ታዳሚውም በጭብጨባና በዕልልታ ደግፎታል።

በመጨረሻም አርቲስት ቤዛ ታደሰ እጅግ ልብ የሚነካ እንጉርጉሮ ስታቀርብ፣ በቅድሚያ የሃይማኖት አባቶቹ ቀድሞ ከተለኮሱት 28 ሻማዎች ላይ በመለኮስና ለታዳሚው በማቀበል የሻማ ማብራት ሥነ ሥርዓት ተካሂዶ፣ 6ፒ ኤም የጀመረው ዝግጅት 9 ተኩል ላይ ተጠናቋል።

The post በአትላንታ ጆርጂያ የሻማ ማብራትና የጸሎት ሥነ ሥርዓት ተካሄደ appeared first on Zehabesha Amharic.


በሊቢያ፣ በየመንና በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ እየተደረገ ያለውን ግፍ ለመቃወምና የሻማ ማብራት ጥሪ በዳላስ

$
0
0

dallas ethiopian zehabesha
በዳላስ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የጋራ መረዳጃ ማህበር የተዘጋጀ ታላቅ የስብሰባ ጥሪ
በሊቢያ፣ በየመንና በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ እየተደረገ ያለውን ግፍ ለመቃወምና የሻማ ማብራት (Candle Vigil) ስነ ስርዓት ለማድረግ ታላቅ ስብሰባ ተዘጋጅቷል። በነቂስ ወጥተን በአሸባሪው ISIS ጭካኔ መስዋዕት የሆኑትን ወገኖቻችንን ለማሰብና በህይወት ያሉትን ወገኖቻችንን ለመታደግ መደረግ የሚገባውን ሁሉ እናድርግ።

The post በሊቢያ፣ በየመንና በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ እየተደረገ ያለውን ግፍ ለመቃወምና የሻማ ማብራት ጥሪ በዳላስ appeared first on Zehabesha Amharic.

“በጣም ደህና ነኝ…ምንም አልሆንኩም”–ወንድም ጥበቡ ወርቅዬ (Video)

የት ሄደን እናልቅስ ?

$
0
0

yilikal
የት ሄደን እናልቅስ
የት ሆነን እንተንፍሰ
የወንድሞቼን ደም የት ሄጄ ልመልስ
ሀገር ነበር እኮ ሁሉንም ማስረሻ
ሀዘን ይሁን ስጋት ከሁሉ መሸሻ
ወንድሜ ሲቃጠል በሳውዝ አፍሪካ ላይ
ስጋዬ ቢታረድ በሊብያ ምድር ላይ
እህቴንም ባጣት በዛ በየመን ላይ
ሀዘኔ ቢበዛ ውስጤ ቢቆስልብኝ
መንግስት እንደሌለው ማንም ሲገልብኝ
ምንም እንኳን ባጣ ሄዶ ሚያተርፍልኝ
ደርሶ ሚያስጥልልኝ
እኔው ተነሳሁኝ እህህ ልለው
ሀዘኔን ቁጭቴን ሁሉን ላሳውቀው
አቅሜም እንኩዋን ባልችል ባልሆን ከጎናቸው
ሀዘኔን በሀገሬ ፍቅሬን ላሳያቸው
ሆ ብዬ ተነሳው በኢትዮጵያ ምድር ላይ
በጀግኖቻችን ደም በፀናች ሐገር ላይ
በእንባዬ እየታተብኩ በህዝቦቼ ስቃይ ጉዞዬን ጀመርኩኝ ወደ አደባባይ
መንግስት እንኮን ራርቶ ወደ ህዝቡ እንዲታይ
ድንገት ሳላስበዉ ምኑንም ሳላውቀው
በእንባዬ እየታተብኩ ጉዞዬን ስጎዘው
መጣብኝ ወገኔ እኔኑ ሊመታ
በሐዘን ላይ ሐዘን ወደ ኔ ሊያመታ
እጅን አነሳኝ እግሩን ዘረጋብኝ
በጣም በጭካኔ ዱላ አሳረፈብኝ
ላዝን የወጣሁት ለ ገዛ ደማችን
አማራ ይሁን ትግሬ አንድ ነው ሕዝባችን
እስላም ክርስቲያኑ አንድ ነው ኑሮአችን
ኢትዮጵያዊነት ነው የኛ መለያችን
ምነው ጨከንክ ወገን በገዛ ደምክ ላይ
እናትክ በእንባ እንዲ ስትሰቀይ
ዋይ! ዋይ! ስትል እምዬ ልጇ ተበልቶባት
አንተ ግን መተካት በእርግጫ ገፋካት
የ 9 ወር ቤትን እማን እረሳካት
ቆም ብዬ ሳየው ማዝነው ለ ራሴ ነው
ግንምን ዋጋ አለው ሚያዝንበት ለሌለው ።

ገጣሚ ፍፁም
ከ ደቡብ አፍሪካ

The post የት ሄደን እናልቅስ ? appeared first on Zehabesha Amharic.

በሊቢያው የጀልባ አደጋ አንድ ኢትዮጵያዊ መሞቱ ተረጋገጠ

$
0
0

libya ethiopia
ባለፈው እሁድ ከሊቢያ ወደ ጣሊያን ከ900 በላይ የተለያዩ አገራት ስደተኞችን አሳፍራ ስትጓዝ በሜዲትራኒያን ባህር የመስጠም አደጋ በደረሰባት ጀልባ ከሞቱት መካከል አንዱ በአዲስ አበባ የኮተቤ ነዋሪ የነበረው እንዳልካቸው አስፋው ይገኝበታል፡፡ በታክሲ ረዳትነትና ሹፌርነት ይተዳደር የነበረው እንዳልካቸው፤ ኑሮን ለማሸነፍ የተሻለ ስራ ፍለጋ የዛሬ 6 ዓመት ወደ ሱዳን ማቅናቱንና እዚያ ለ5 ዓመታት ከቆየ በኋላ ከዓመት በፊት ሊቢያ መድረሱን ደውሎ እንዳሳወቃቸው ቤተሰቦቹ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ “ለረጅም ጊዜ ድምፁ ጠፍቶብን ነበር” የሚሉት ቤተሰቦቹ፤ በሊቢያ ያለው ሁኔታ አስጨናቂ እየሆነ ከመጣበት ጊዜ አንስቶ በሃሳብና በሰቀቀን ‹እንዴት ሆኖ ይሆን?› እያሉ ድምፁን ለመስማት በመናፈቅ ወደ ፈጣሪያቸው ይለማመኑ እንደነበር ይገልፃሉ፡፡ በመጨረሻቡ ባልጠበቀው ሁኔታ እንደወጣ የቀረውን የእንዳልካቸውን ህልፈት የሰሙት ባለፈው ረቡዕ መሆኑን ወንድሙ ሙሉጌታ አስፋው ተናግሯል፡፡ የእንዳልካቸውን ህልፈት በስልክ ለቤተሰብ ያረዱት ለቀጣዩ የባህር ጉዞ ተረኛ የነበሩና እርሱን በቅርበት የሚያውቁት ስደተኞች ናቸው፡፡ “ወንድማችን ሱዳን ውስጥ ሲኖር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ራሱን ያስተዳድር ነበር” የሚለው የሟች ወንድም፤ ባጠራቀመው ገንዘብ የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ወደ አውሮፓ ለመሻገር ጥረት ሲያደርግ ባደረገበት አጋጣሚ ከቤተሰቡ እንደተነፋፈቀ መቅረቱ ለቤተሰቡ መሪር ሀዘን እንደሆነበት ተናግሯል፡፡ “ዴይሊ ሜይል” ጀልባዋ 950 ኤርትራዊያን፣ ኢትዮጵያውያንና ሶማሊያውያን ስደተኞችን አሳፍራ ስትጓዝ መስጠሟን የዘገበ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 200 ያህሉ ሴቶች እንደነበሩ ጠቁሟል፡፡ ከአደጋው የተረፉት 28 ብቻ መሆናቸውን የዘገበው ጋዜጣው፤ ሲሆኑ አስክሬናቸው የተገኘው የ20ዎቹ ብቻ ነው ብሏል፡፡ “አልጀዚራ” እና “ዘ ጋርዲያን” በበኩላቸው ጀልባዋ 700 ስደተኞችን አሳድራ እንደነበር ጠቁመውየተረፉት 28 አስከሬናቸው የተገኘው 20 ብቻ መሆኑን ዘግበዋል፡፡ አደጋው የተፈጠረው በጀልባዋ ላይ ተፋፍገው የተጫኑት ስደተኞች በርቀት ሌላ የንግድ መርከብ
ተመልክተው ጥሪ ለማቅረብ ሲሉ በፈጠሩት ግርግር ጀልባዋ ሚዛኗን በመስጠሟ ነው ብለዋል ዘገባዎች፡፡
ከአደጋው የደረሰው ከሊቢያ የባህር ዳርቻ 96 ኪ.ሜ እንዲሁም ከጣሊያኗ የስደተኞች መዳረሻ
ላምፔዱሣ ደሴት 193 ኪ.ሜ ርቀት ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡

ምንጭ አዲስ አድማስ

The post በሊቢያው የጀልባ አደጋ አንድ ኢትዮጵያዊ መሞቱ ተረጋገጠ appeared first on Zehabesha Amharic.

በአይሲስ የተጣሰው የቁርአን ቃል –“ሙስሊም ባልሆኑ ንፁሃን ሰዎች ላይ ግድያ የፈፀመ ሰው የጀነትን እጣን አያሸትም”

$
0
0

ኑርሁሴን እንድሪስ

በሁለቱ ታላላቅ እምነቶች ውስጥ (ክርስትና እና እስልምናን ማለቴ ነው) ለሰው ዘር በሙሉ የተላለፈ አንድ መለኮታዊ መልዕክት አለ፡፡ ይህ መልዕክት በሁለት ቅዱሳን መፃህፍት ውስጥ ቢገኝም መልዕክቱ ግን ተመሳሳይ ነው፡፡ የሰው ልጅን ነፍስ ማጥፋት የተወገዘ ተግባር መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ እና ቁርአን ያወሳሉ፡፡ ይህን መልዕክት ለሰው ልጆች የላከው ደግሞ የሰማይና የምድር ፈጣሪ እንዲሁም የሰው ልጆችን ጨምሮ በሁለቱ መካከል ያሉትን በሙሉ ያስገኘው አምላክ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ምዕራፎቹ ውስጥ የሰው ልጅ ግድያን ይከለክላል፡፡ በማቲዎስ 5፡21፣ ምፅአት 20፡13፣ ሮሜ 13፡14፣ ዘፍጥረት 9፡5-6 … ወዘተ፤ በጣም ብዙ አንቀፆች ሰውን መግደል የማይፈቀድ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ በማቲዎስ 5፡21 ውስጥ የሰፈረው ቃል እንዲህ ይላል፡-

(Photo File)

(Photo File)


“… አትግደል፤ የገደለ ሰው ይፈረድበታል …”
በቅዱስ ቁርአን ውስጥም የሰው ልጅን ነፍስ ማጥፋት ትልቅ ሀጢአት መሆኑ በብዙ አንቀፆች ውስጥ ፍሮአል፡፡ በአል-ሙምታሐና፡8፣ በአል-ኒሳ 89—91፣ በአል-በቀራ፡ 190፣ በአል-አንኢም፡151…
ውስጥ የመግደልን አስከፊነት ያነሳል፡፡ በአል-ማኢዳ፡32 ውስጥ የሰፈረው እንዲህ ይነበባል፡- “… አንድ ነፍስን የገደለ ሰው መላውን የሰው ዘር እንዳጠፋ ይቆጠራል፤ አንድ ነፍስን ያዳነ ሰው መላውን የሰው ዘር እንዳዳነ ይቆጠራል…”

በእስልምናም ሆነ በክርስትና እምነቶች ውስጥ የመግደልን አስከፊነት የሚገልፁ የአምላክ ቃላቶች ተቀምጠዋል፡፡ ምዕመናን ከዚህ ክፉ ተግባር እንዲቆጠቡም ሐያሉ አምላክ አዟል፡፡ ነገር ግን በእስልምናም ሆነ በክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች በርካታ የግድያና የሽብር ተግባሮች መፈፀማቸውን ታሪክ ይነግረናል፡፡ እንደ ፖለቲካ ተመራማሪዎች ከሆነ፤ የሽብርተኝነት ዋና አላማ በመንግስት አልያም በሆነ አካል ላይ ተፅዕኖና ማስገደድን መፍጠር ነው፡፡ ሽብርተኝነት ከማንኛውም ሀይማኖት ጋር የሚገናኝ አይደለም። አንዳንድ ጊዜ ፍትህ ያጡ ግለሰቦች የሚከተሉት ተግባር ሲሆን ሌላ ጊዜ ደግሞ የፖለቲካ አላማን ያነገቡ ቡድኖች ፈፅሙት ነው፡፡ ሃይማኖቶች መግደል ክልክል መሆኑን የሚገልፁ ከሆነ ታዲያ ለምንድነው ሃይማኖተኞች የሚገድሉት? ግድያና ሽብር ማካሄድ የሚገናኘው ከሃይማኖት ጋር ነው ወይስ ከፖለቲካ? የተለያዩ እምነቶችን የሚያራምዱ የአለማችን ሰዎች በደርዘን የሚቆጠሩ ግድያና ሽብሮችን በንፁሐን ዜጎች ላይ ፈፅመዋል፡፡ ለምሳሌ በ2011 ዓ.ም የቀኝ ክንፍ ክርስቲያን አክራሪ የሆነው አንደርስ ብሪቬክ በኖርዌይ 77 ሰዎችን ገድሏል፡፡ ብሪቬክ ከፍተኛ የሆነ የእስልምና ሃይማኖት ጥላቻ እንደነበረው በወቅቱ ተገልጿል፡፡ በ2013 ዓ.ም የሶማሊያ ሙስሊሞች በዌስትጌት የገበያ ሞል ውስጥ ቦንብ አፈንድተው የ67 ሰዎችን ህይወት ቀጥፈዋል፡፡ በ1955 ዓ.ም በኦክላሐማ ከተማ ውስጥ የፈነዳው ቦንብ 166 ንፁሐንን ገድሏል፡፡ ድርጊቱን የፈፀሙት ደግሞ ቲሞቲ እና ቴሪ የተባሉ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ በ2002 ዓ.ም በባሊ ደሴት ላይ የፈነዳው ቦንብ የ202 ዜጎችን ነፍስ በልቷል፡፡ ድርጊቱን የፈፀሙት ጀማህ ኢስላሚያ የተባሉ የእስልምና ተከታዮች ናቸው፡፡ በ2004 ዓ.ም የሰሜን ምስራቅ ህንድ ክርስቲያኖች ድርጅት 44 ሰዎችን ገድሏል፡፡ በ2001 ዓ.ም የተጠለፈ አውሮፕላን በዓለም የንግድ ድርጅት ህንፃ ላይ ተጋጭቶ 3000 ንፁሐንን ገድሏል፡፡ ተግባሩን የፈፀሙት የአልቃኢዳ ሙስሊሞች ነበሩ፡፡
በ2015 በጋሪሳ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የአል-ሻባብ ሙስሊሞች 148 ኬንያውያንን ገድለዋል፡፡

በ1972 ዓ.ም የካቶሊክ እምነት ተከታዮች የሆኑት የአይሪሽ ሪፐብሊካን አርሚ ቡድኖች በለንደን 47 ሰዎችን በቦንብ ፈጅተዋል፡፡ እነዚህን የመሰሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሽብርና ግድያዎችን በሁለቱም እምነቶች ውስጥ የሚገኙ ቡድኖችና ግለሰቦች ፈፅመዋል፡፡ ይህ የሚያሳየው ደግሞ ሽብርና ግድያ ባለቤትነቱ የማንም ሃይማኖት አለመሆኑን ነው፡፡ የቀድሞ የግብፅ ሙፍቲ ሼክ አሊ ጎማኢ እንደተናገሩት፤ “ሽብርተኝነት ሃይማኖት የሚወልደው ጉዳይ አይደለም፡፡ ሽብርተኝነት የብልሹ አስተሳሰብ ውጤት ነው፡፡ ሽብርተኝነት፣ የእብሪተኝነትና አጥፊነት መገለጫ ነው፡፡ ብልሹነት፣ እብሪተኝነትና አጥፊነት ከመለኮታዊ ልቦና ጋር የሚገናኙ አይደሉም፡፡” ራሱን የእስልምና መገለጫ አድርጎ የሚንቀሳቀሰው አይሲስም የግብፁ ሙፍቲ በተናገሩት ውስጥ የሚፈረጅ መሆኑን ተግባራቱ ያሳያሉ፡፡ ባለፈው እሁድ በ28 ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈፀመው አሰቃቂ ግድያ አላማው ግልፅ አይደለም፡፡ አይሲስ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ምን አይነት ቅያሜ ውስጥ ቢገባ ይሆን 28 ዜጎቿን የፈጀው? ለሚለው ጥያቄም መልስ የለውም። አይሲስ የገደላቸው
ኢትዮጵያውያን ክርስቲያን በመሆናቸው ብቻ ነው እንዳንል በማግስቱ 24 የኢራቅ ሙስሊሞችን ገድሏል፡፡ ለዚህም ነው የአይሲስ አላማና መገለጫ የግብፁ ሙፍቲ ከተናገሩት ጋር ይገናኛል ያልኩት፡፡ አይሲስ ሙስሊም ክርስቲያን ሳይል በሰው ዘር ላይ የዘመተ አረመኔ ቡድን መሆኑ አያጠራጥርም፡፡

አይሲስ የሸሪአ ተከታይ ነው ከተባለ ለምንድነው ታዲያ በቁርአን ውስጥ የሚገኘውን አል-ማኢዳ፡32
የጣሰው? “አንድ ነፍስን ያጠፋ መላውን የሰው ዘር እንዳጠፋ ይቆጠራል፤ አንድ ነፍስን ያዳነ መላውን የሰው ዘር እንዳዳነ ይቆጠራል፡፡” የሚለው መለኮታዊ ቃል ለምንድነው በአይሲስ ያልተከበረው? የሰው ነፍስን አጥፍቶ ጀነትን መመኘት የዋህነት ይመስለኛል፡፡ በታላቁ መምህር በነብዩ ሙሀመድ የህይወት ፈለግ ውስጥ የዚህ አይነቱ ርዕዮት በፍፁም የተወገዘ ነው፡፡ በቡካሪ ሐዲስ ውስጥ ነብዩ ሙሀመድ የተናገሩት ይህን ይመስላል፡-

“ሙስሊም ባልሆኑ ንፁሐን ሰዎች ላይ ግድያ የፈፀመ ሰው የጀነትን እጣን አያሸትም” ንፁሐን ሰዎች ላይ ግድያ ፈፅመን ጀነት መግባት የምንመኝ ከሆነ ካሁኑ እርማችንን ማውጣት አለብን፤ ነብይ ሽታውን እንኳን እንደማናገኘው አርድተውናልና፡፡ በእስልምና ሐይማኖት ውስጥ ጥልቅ እውቀት ያለው አይሲስ ወይስ መልእክተኛው ሙሐመድ? አይሲስ የሚያራምደው እስልምና ከየት የመጣ ይሆን? ነብዩ ካስተማሩትና ካዘዙት የእስልምና እውቀት ውጭ ከየት ሊመጣ!

The post በአይሲስ የተጣሰው የቁርአን ቃል – “ሙስሊም ባልሆኑ ንፁሃን ሰዎች ላይ ግድያ የፈፀመ ሰው የጀነትን እጣን አያሸትም” appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live