Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ቢፍቱ በሲያትል በስለት ተወግታ ሕይወቷ አለፈ

$
0
0

biftu

(ዘ-ሐበሻ) ስሟ ቢፍቱ ዳዲ ይሰኛል:: የተወለደቸው እዚሁ ሰሜን አሜሪካ ውስጥ ይሁን እንጂ ቤተሰቦቿ ከኢትዮጵያ ናቸው:: እንደ ሲያትልፒ ድረገጽ ገለጻ ከሆነ ቢፍቱ ዳዲ በስለት የተወጋችው ማርች 9 ቀን 2015 ነው::

በሲያትል ዋሊንግፎድ መኖሪያ ሰፈር አካባቢ ገና በ24 ዓመቷ በስለት የተወጋቸውና ሕይወቷ ያለፈው ቢፍቱ ከቆመ መኪና ጀርባ ነው::

የወጡት ዜናዎች እንደሚጠቁሙት ይህች ወጣት እዚያው ሲያትል ዋሽንግተን ውስጥ በስትሪፕ ክለብ (በምሽት ዳንስ ቤት) ትሰራ ነበር::

የኪንግ ካውንቲ ፖሊስ የጠረጠረው የቢፍቱ ገዳይ ነው የተባለው ተከሳሽ ሪቻርድስ ቢፍቱን ከመግደሉ በፊት በምትሰራበት ስትሪፕ ክለብ (የምሽት ዳንስ ቤት) አካባቢ ሲጨቃጨቁ ነበር ብሏል:: የሚያውቋት ሰዎች ለፖሊስ እንደገለጹት ቢፍቱ ወደ ሥራዋ ዳንስ ቤት በምትሄድበት ወቅት ብዙ ጊዜ የህመም ማስታገሻ መድሃኒቶችን ትወስድ ነበር::

ፖሊስ ከሪቻርድ ጋር ትጨቃጨቅ እንጂ በምን ምክንያት ሊገድላት እንደቻለ የሰጠው መግለጫ የለም:: ለሟች ነብስ ይማር እንላለን::

The post ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ቢፍቱ በሲያትል በስለት ተወግታ ሕይወቷ አለፈ appeared first on Zehabesha Amharic.


(ዜና ፎቶ) የኦሮሞን ሕዝብ “ልክ እናስገባዋለን”ያሉት አባይ ጸሐዬ በኦህዴድ ስብሰባ ላይ እንቅልፋቸውን ተኙ

$
0
0

በቅርቡ የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን ማስፋፋት ተከትሎ የኦሮሞ ተማሪዎች ያነሱትን ተቃውሞና መንግስታቸው ሕዝቡን በመግደል ጭምር እርምጃ በመውሰድ ተቃውሞውን ለማርገብ የሞከሩት የሕወሓቱ ቁልፍ ሰው አባይ ጸሐዬ ካሁን በኋላ የኦሮሞ ሕዝብ በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ላይ ጥያቄ ቢያነሳ “ልክ እናስገባዋለን; ያሰብነውንም እናደርጋለን” ማለታቸው በድምጽ ወጥቶ በዘ-ሐበሻ ድረገጽ እና በተለያዩ ድረገጾች ላይ መውጣቱ አይዘነጋም:: ሕወሓቱ አባይ ጸሀዬ ከኦህዴድ አመራሮች ጀርባ ሆነው የኦሮሚያ ክልልን የሚያሽከረክር ሲሆን ሰሞኑን ኦህዴድ 25ኛ ዓመቱን በሚያከብርበት በዓል ተገኝተው ነበር:: አባይ ጸሐዬ ሕዝቡን ልክ እናስገባዋለን ማለታቸው ሳያንስ የንቀታቸው ንቀት በስብሰባው ላይ የኦህዴድ አመራሮች ንግግር ሲያደርጉ እንቅልፋቸውን ለጥጠውታል:: ይህም በፎቶ ግራፍ ተደግፎ ለዘ-ሐበሻ ደርሷል:: ተካፈሏቸው:-
abay
abay Tsehaye

The post (ዜና ፎቶ) የኦሮሞን ሕዝብ “ልክ እናስገባዋለን” ያሉት አባይ ጸሐዬ በኦህዴድ ስብሰባ ላይ እንቅልፋቸውን ተኙ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢትዮጵያ የአባይ ግድብ ግንባታን በየደረጃው የሚቆጣጠረውን ስምምነት ፈረመች

$
0
0

ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ በጋራ የፈረሙት አዲሱ ስምምነት ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ በሙሉ ነጻነት የምትሰራውን ስራ እንደሚገድብ ከአረብኛ ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመው ሰነድ አመልክቷል።

ሰነዱ ኢትዮጵያ ግድቡን ለመገንባት በምታደርገው ማንኛውም እንቅስቃሴና በየትኛውም የግንባታ ደረጃ ላይ አለማቀፉ አጥኝ ቡድን ለሚሰጠው አስተያየት ተገዢ በመሆን እንድትተገብር ይገልጻል። አጥኝ ኮሚቴው የግድቡ ግንባታ የግብጽንና ሱዳንን የውሃ ድርሻ መጠን
ይቀንሳል ወይም በግብጽና ሱዳን አካባቢያዊ ሁኔታ ላይ ተጽአኖ ያመጣል የሚል ድምደማ ላይ ከደረሰ ካሳ እስከመክፈል የሚያደርስ ግዴታም መጣሉ ተመልክቷል።
Blue Nile 2
አጥኚ ቡድኑ የመጨረሻውን የጥናት ውጤት ይፋ ካደረገ በሁዋላ ሶስቱም አገራት እንደሚቀበሉት የተስማሙ ሲሆን፣ ምናልባት አጥኝ ቡድኑ ግድቡ በግብጽና ሱዳን ላይ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግር ያስከትላል ብሎ ቢወስን ኢትዮጵያ የግድቡን ቅርጽ እስከመቀየር ልትደርስ ትችላለች።
ኢትዮጵያ የምትገነባው ግድብ፣ ከግብጽና ሱዳን የውሃ ማጠራቀሚያዎችን የሚጎዳ ከሆነም ኢትዮጵያ አገራቱን ፈጥና የማሳወቅና ለውጥ ማድረግ እንደሚኖርባትም ስምምነቱ ይገልጻል።

የስምምነቱ አብዛኛው ክፍል ኢትዮጵያ ስለምትፈጽማቸው ግዴታዎች ትኩረት ያደረገ ነው። ግብጽና ሱዳን ለአባይ ወንዝ የሚያበረክቱት የውሃ ድርሻ ካለመኖሩ አንጻር ስምምነቱ በዋነኝነት ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን መብት የሚገድብ ብቻ ሳይሆን፣ የአባይ ግድብ
ግንባታ እጣ ፋንታን ከኢትዮጵያ እጅ አውጥቶ በአለማቀፍ አጥኚዎች እጅ እንዲሆን የሚያደርገው ነው በሚል ትችት እየቀረበበት ነው።
ይሁን እንጅ ሶስቱም አገራት ስምምነቱን በማወደስ ለተግባራዊነቱ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

The post ኢትዮጵያ የአባይ ግድብ ግንባታን በየደረጃው የሚቆጣጠረውን ስምምነት ፈረመች appeared first on Zehabesha Amharic.

የዲያቆን ዳንኤል ስሜታዊ ትንታኔና መሬት ላይ ያለው እዉነታ ! የመጨረሻ ክፍል –አብዱላህ

$
0
0

daniel-kibret-300x207ዲ/ዳንኤል አክራሪ ያሉዋቸው ሰለፊስቶች የሃገራችንን ነባር እስልምና ተከታዮች ቅዱሳን የማይቀበሉ ፅንፈኞች ናቸው ሲሉ አውግዘዋቸዋል። እዚህ ላይ የተቆረቆሩላቸው ለማስመሰል የሞከሩትን የቀድሞዎቹን ሙስሊሞች በዚሁ ንግግራቸው ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር አብረው ሃገር ያደሙ በማለት ሲወነጅሏቸው እንደነበር አድማጭ የዘነጋ ይመስል የዛሬዎቹን ሙስሊሞች ዉንጀላ ጎላ ለማድረግ ለቀድሞዎቹ አጋዥ መስለው ቀርበዋል።

ለነገሩ በቀዳሚነት ሊያሳስባቸው ይገባ የነበረው በሃገራችን የተዋህዶ ኦርተዶክስ ቤተክርስቲያን የምታመልካቸውን ቅዱሳን ከማስተባበል  አልፈው የቲዮሎጂ ስነ-ምግባር በጎደለው መልኩ መሳለቂያ እያደረጉ ያሉት አንዳንድ የሃገራችን የፕሮቴስታንት ፓስተሮች ድርጊትና የእርሳቸው እምነት ውስጥ ጉዳዩ ያስከተለው የመከፋፈል ችግርን ነበር ። በዚህም ድርጊታቸው ለአድማጮቻቸው ያላቸን ከፍተኛ ንቀት ይፋ አድርገዋል ።

በንግግራቸው ያነሱት ሌላው ጉዳይ አክራሪዎች የሚሏቸው በአክሱም መስጅድ እንዲገነባ ጥያቄ ማቅረባቸውን ነው።  ከንግግራቸው ለመረዳት የቻልኩት አክሱም ፅላት ያረፈባት ስፍራ በመሆኗ የእስልምና እምነት የአምልኮ ስፍራውን ያረክሰዋል በሚል ህሳቤ ነው። ለዚህ አስተሳሰብ መንስኤው አክሱም ፅድቅነቷ እንዲጠበቅ ከሚያረክሷት ነገሮች የጸዳች ልትሆን ይገባል ከሆነ እስኪ የሚከተሉትን እውነታዎች በሚዛናዊነት ለመዳኘት እንሞክር።

  • ሁላችንም የምንኮራባቸው የአክሱም ስልጣኔ መገለጫ ግዙፎቹ ሃዉልቶች ዛሬም የቀደምት ህዝቦቻችን እምነት የሆነውን የጣኦት አምልኮ አሻራን እንደያዙ በአክሱም ከተማ ይገኛሉ። እንደ ማንኛዉም  ኢትዮጵያዊ እነዚህ ቅርሶቻችን በተገቢው መንገድ እንዲጠበቁ እፈልጋለሁ ። እዚህ ላይ ግልጽ እንዲሆን የፈለኩት ነጥብ አክሱም ፅድቅነቷ እንዲጠበቅ እንፈልጋለን ባዮች አንድን ቅዱስ ስፍራ ከጣኦት አምልኮ መገለጫ ቅርሶችና ድርጊቶች  በላይ  እንዴት ሆኖ አንድ አምላክ የሚመለክበት መስጂድ ሊያረክሰው ይችላል ? የሚለዉን ነዉ ።
  • የአክሱም ከተማ በርካታ ቁጥር ያላቸው ቱሪስቶች መዳረሻ መሆኗ ይታወቃል። ከዚህም ጋር በተያያዘ መልኩ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዳንኪራ  እና ዝሙት የሚፈፀምባቸው ቤቶች በከተማይቱ ውስጥ ይገኛሉ። ዝሙት ደግሞ በመፅሃፍ ቅዱስ ከተወገዙት ሃጥያቶች አንዱ ነው።  በእውን ለከተማይቷ ቅድስና የምንቆረቆር ከሆነ ከዚህስ የባሰ የሚያረክስ ጉዳይ ይገኛልን ?

ከላይ የጠቀስኳቸውን ነጥቦች በሚዛናዊነት ከዳኘን በአክሱም  የሙስሊሞችን የፀሎት ቦታ መገንባትን የሚቃወሙ ግለሰቦች ለዚህ ሀሳብ ያነሳሳቸው ዋና ምክንያት መንፈሳዊ ገፅታው እንዳልሆነ ለመረዳት አያዳግትም።  ይህ ካልሆነ ደግሞ ተቃውሞው ያነጣጠረው የዜጎችን መብት በመግፈፍ ላይ መሆኑ ግልፅ ነው ።

በሃገራችን ህገ-መንግስት አንቀፅ 27  ዜጎች የአምልኮ ስፍራቸውን በነጻነት የመገንባት መብታቸው የተጠበቀ ሆኖ ሳለ ይህን የጠየቁ የአካባቢው ተወላጆችን እና ነዋሪዎችን እንደ ፅንፈኛ መቁጠር ህገ-መንግስታዊ መብትንና ሃገራችን በፈረመቻቸው ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶች የተከበሩ ተመሳሳይ መብቶችን  ማስተባበል ጭምር መሆኑን ሊያውቁት ይገባል።

ዲያቆኑ የአክራሪዎች ሌላው መገለጫ ያሉት “ኢትዮጵያ የክርስትያን ደሴት ነች ”የሚለውን ሃሳብ መቃወማቸው ነው በማለት በሃገራችን   ኢትዮጵያ የእኩል ባለቤትነት መብት እንዳላቸው የሚገልጹ ሙስሊሞችን ለማሸማቀቅ  ሙከራ አድርገዋል ።  ይህን አስተሳሰብ ከታሪክም ሆነ ከዜጎች መብት አኳያ መመርመሩ ግንዛቤ ሊያስጨብጥ ስለሚችል የሚከተሉትን ነጥቦች ማየት አስፈላጊ ሆኖ አግኝቸዋለሁ።

የዲ/ ዳንኤልን አጠቃላይ ፅሁፉቸው አንኳር ነጥብ ያነጣጠረው ሙስሊሙን ማህበረሰብ ከሌላ ስፍራ መጥቶ  የሃገር ባለቤት በሆነው የክርስትያን ህዝብ መልካም ፈቃድ በአገሪቱ የሰፈረ ውለታ የተዋለለት ባዕድ ህዝብ አድርጎ መሳልን ነው።  ይህ ህሳቤ መሰረቱ ክርስትናን ሃገር በቀል እስልምና ግን መጤ አድርጎ በመሳል ላይ የተመሰረተ ታሪክን ያዛባ አቀራረብ ነው።  እውነታው ግን ክርስትናም ሆነ እስልምና በመካከለኛው ምስራቅ የበቀሉ እና ወደ ሃገራችን ኢትዮጵያ የገቡ መሆናቸው ነው።  ሁለቱንም እምነቶች የተቀበሏቸው  ሃገር በቀል ህዝቦች ናቸው።  ለዘመናት በግልፅም ሆነ በተዘዋዋሪ መልኩ ሲነገር የቆየው እና በህብረተሰብ ውስጥ ለማስረፅ የተሞከረው ህሳቤ ዛሬ ላይ ዲ/ ዳንኤል የደገሙት የተዛበ የታሪክ አቀራረብ ነው። ይህ ህሳቤ ሙስሊሙ እና ክርስትያኑ ማህበረሰብ እኩል የሃገር ባለቤት እና እኩል የሃገር ተቆርቋሪ መሆናቸዉን በማስተባበሉ በጋራ – ለጋራ መብት እንዳይነሳ ማነቆ ሆኖ ቆይቷል።  ዛሬም ይህንኑ ክፍተት ለማስፋት እና የዜጎችን ለጋራ መብት አብሮ መነሳት ለማኮላሸት በሃይማኖት አባትነት ካባ የተሸፈነ አጀንዳ እያራመዱ መገኘታቸው ነው።

ከዚህ  መረዳት እንደሚቻለው ኢትዮጵያ ሃገራችን ዲ/ዳንኤል እንደሚሉት የአንድ እምነት ተከታይ ህዝቦቻችን ብቻ ሃገር ሳትሆን የሁላችንም ኢትዮጵያውያን ሃገር መሆኗን ነው። ባለንበት በ 21ኛዉ ክፍለ ዘመን ሃገራችን ኢትዮጵያ የክርስትና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ሃገር ነች ለማለት የደፈሩት ዲ/ ዳኒኤል ኢትዮጵያ የጋራ ሃገራችን ነች የሚለዉን ሙስሊም ወገናቸውን አክራሪ ብለው መወንጀላቸው ለምን ይሆን ? አባባላቸው ቀዳማዊ ሃይለስላሴ  እኛ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች እንደ ኢትዮጵያዊ ዜጋ የማንቆጠርና ይልቁንም የክርስቲያኖች ሃገር በሆነችዉ ኢትዮጵያ የምንኖር መሆናችንን እንዳንዘነጋ በየንግግሮቻቸው “በኢትዮጵያ የሚኖሩ ሙስሊሞች ” እያሉ ይጠሩን የነበረውን አስታወሰኝ ። ልንዘነጋው በማንችለው መልኩ በልቦናችን ይሰርፅ ዘንድ በተረትና ምሳሌ ሳይቀር “የአሞራ ቤቱ ዋርካ የእስላም አገሩ መካ” ሲሉም እንሰማለን።  ታዲያ ዲ/ ዳንኤል ይህን ከቀደምት ነገስታቶቻችን ካባ ጎን ለጎን በሙዚየም መቀመጥ ያለበትን ዘመን የሚጠየፈውን ህሳቤ የማንቀበል እና በአገራችን ኢትዮጵያ የእኩል ባለቤትነት መብት ይገባናል ባይ ሙስሊም ኢትዮጵያዊያንን አክራሪ ሲሉ መወንጀላቸው ምንን ያመላክታል?

ከታሪክ አኳያ፡-

አገራችን ኢትዮጵያ የረዥም ዘመን ታሪክ ያላት አገር ነች።  በተለያዩ  የታሪክ ዘመናትም የተለያዩ የግዛት ክልሎች የነበሯት።  በውስጧ የኖሩባትም ህዝቦች የተለያየ የዘር እና የሃይማኖት ስብጥር ፣  የስልጣኔ ደረጃ ፣ የአስተዳደር ስርዓት ወዘተ  ነበራቸው ።

በሃገራቸን 3000 ዘመን ታሪክ ውስጥ፡-

  • የመጀመርያዎቹ 1300 ዓመታት ከክርስቶስ ልደት በፊት 900 አመታት እና ከእየሱስ ውልደት በሁዋላ 400 ዓመታት የጣኦት አምልኮ ተከታዮች እና የኋላ ኋላ የተቀላቀሏቸው የይሁድ እምነት ተከታይ ህዝቦቻችን የኖሩባት ሲሆን እነሱም ሁላችንም የምንኮራበትን የአክሱም ስልጣኔን ያስመዘገቡ እና በቅርስነት አስደናቂ ሃውልቶችን ትተውልን አልፈዋል።
  • በመቀጠልም የክርስትና እምነትን የተቀበሉ ህዝቦቻችን በ4ኛው ክፍለ ዘመን ከጣኦት አምልኮ ተከታዮች የወረሱትን ስልጣኔ ለ100 ዓመት ካሳደጉት ቡሃላ በ5ኛው ክፍለ ዘመን ስልጣኔው ማሽቆልቆል የጀመረ ሲሆን በ960 በዮዲት ድል እንደተደረገ በታሪክ ተዘግቧል
  • በማስከተልም የኩሽ ህዝቦች ዝርያ የሆነው የዛጉየ ስረዎ-መንግስት በ1137 -1270 የተተካ ሲሆን እነዚህ የአገው ህዝቦች የላሊበላን ገዳማት እና አብያተ ክርስትያናት በቅርስነት ትተውልን አልፈዋል
  • ከዛጉየ ቀጥሎ የነበረው የንግስና ስርአት ሰለሞናዊው ስርዎ-መንግስት ሲሆን ይህ ስርዎ-መንግስት ከ1270 ጀምሮ የነበረ እና የግዛት ክልሉም በዛሬው ሰሜናዊ የሃገራችን ክልል ላይ ብቻ የተወሰነ ነበር

 

ከላይ የተዳሰሰው በዛሬዋ የሃገራችን ሰሜናዊ ክፍል የነበረውን የታሪክ ገፅታ ሲሆን ።  በዛሬው የመካከለኛው ፣ የምስራቅ እና ደቡባዊ የሃገራችን ክፍሎች ደግሞ ከ7ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የተለያዩ የሙስሊም መንግስታት (ሱልጣኔቶች) ነበሩ።

 

  • ከነዚህ ውስጥ የሃረር ሱልጣኔት በ7ኛው እና 11ኛው ክፍለ ዘመን መካከል የተመሰረተ ሲሆን መንግስቷም በንግድ የታወቀና የራሷ ገንዘብም የነበራት ነበረች።  ከተማይቷ በ2006 በዩኔስኮ የአለም ቅርስነት የተመዘገበች ስትሆን ይህንንም ድርሻ ያሰጧት በ10ኛው  ክፍለ ዘመን የተሰሩት ውብ መስጅዶች እና ብዙ የአምልኮ ስፍራዎች ናቸው።  ይህ ማለት ደግሞ ከላሊበላም ሆነ ሌሎች ቆየት ካሉ ታሪካዊ የእምነት ቦታዎች ቀዳሚውን ስፍራ ያስይዛታል።
  • በሁለተኛ ደረጃ የሚቆጠረው የሸዋ ሱልጣኔት ሲሆን ይህም ከ896 እስከ 1283 የኖረ በጉራጌ ህዝቦች የተመሰረተ ስርዎ-መንግስት ነበር። ግዛቱም ከዛሬይቱ አዲስ አበባ 70 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ወለላ ተብላ በምትጠራ ሰሜን ሸዋ አካባቢ   ነበር።  ይህ ንግስና ዘጠኝ ሱልጣኖች በተዋረድ የገዙት እና ከ150 ዓመት በላይ የቆየ እንደነበር የታሪክ ሰነዶች ያሳያሉ።  በፈረንሳይ አርኪዮሎጂስቶች የተገኙ ሶስት የከተማ ፍርስራሽ እና የመስጅድ ቅሪቶች የሸዋን ኢስላማዊ መንግስት የእድገት ደረጃውዋናም ማረጋገጥ ችሏል።
  • በሶስተኛ ደረጃ የሚጠቀሰው የሃድያ ሱልጣኔት ነው። ይህ ሱልጣኔት ከ1300 እስከ 1500ኛው ክ.ዘ የዘለቀ ሲሆን ግዛቱም በዛሬዋ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ  ድንበሩም በሰሜን በኩል የአባይን  ወንዝ የሚነካ ነበር
  • የይፋት ሱልጣኔት በመባል የሚታወቀው ደግሞ ከ1285 እስከ 1415 የኖረው ነው። ይህ በአፍሪካ ቀንድ ታላቅ ተብለው ከሚጠሩት የሙስሊም ሱልጣኔቶች ውስጥ አንዱ ነው።  ግዛቱም ከዛሬዋ ሸዋ ጀምሮ ባሌን ያጠቃለለ እስከ ምስራቅ ጅቡቲ እና ሰሜን ሶማልያን የያዘ እንደነበር እና ማዕከሉም ዘይላ እንደነበር ታሪክ ያብራራል። ሱልጣኔቱ ሰባት ዋና ዋና ከተሞች የነበሩትና በአስተዳደር ረገድም የረቀቀ እንደነበር መዛግብት ያሳያሉ። በዚህ ረገድ የተለያዩ ያልተጠቀሱ የሙስሊም መንግስታት እንደነበሩ መታወቅ ይኖርበታል እንደምሳሌ፡- የአዳል ፣ ባሌ እና ወዘተ

ከላይ የተመለከተናቸው አጠር ብለው የቀረቡት ታሪኮች በግልፅ እንደሚያሳዩት ዛሬ የኛ ትውልድ የሚኮራባቸው ታሪኮቻችን በዛሬው የሰሜኑ የሃገራችን ክፍል የኖሩት የጣኦት አምልኮ ተከታይ ህዝቦች የተዉልን ስልጣኔ 1300 ዓመት እድሜ ያስቆጠረ እንደነበር አይተናል።  ከዛም የክርስትና እምነት ወደ ሃገራችን የሰሜኑ ክፍል ከገባ ቡሃላ የራሱን ድርሻ አበርክቷል።  በተመሳሳይ መልኩ በዛሬው መካከለኛ ፣ ምስራቃዊ እና ደቡባውው የሃገራችን ክፍሎች ደግሞ የእስልምና እምነት የሚከተሉ ህቦቻችን ያበረከቷቸውን ታሪካዊ ስልጣኔዎች እና ቅርሶች ለማየት ሞክረናል። ከዚህ ላይ መረዳት እንደሚቻለው ኢትዮጵያ ሃገራችን ዲ/ዳንኤል እንደሚሉት የአንድ እምነት ተከታይ ህዝቦቻችን ብቻ ሃገር ሳትሆን የሁላችንም ኢትዮጵያውያን ሃገር መሆኗን ነው። ዲያቆኑ ይህን መሰሬታዊ  ነጥብ እንኴ ለመረዳት ያለመቻላቸውን አሳፋሪ ሆኖ አግኝቸዋለሁ ።

የዲ/ዳንኤል ሌሎች የአክራሪነት ክሶች በጥቅሉ፡-  የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን በሃገራቸው ያላቸውን ዜግነት እና ህገ-መንግስታዊ መብቶች የጣሱ ናቸው እንደምሳሌ፡-

  • እርሳቸው ለአፍሪካ እና ለዓለም ሃዋርያነት እራሳቸውን እና ተከታዮቻቸውን ዝግጁ መሆን እንደሚገባቸው ሲሰብኩ ሙስሊም ኢትዮጵያዊ በሃገሩ ወገኖቹን ማስተማሩን እንደ ፅንፈኝነት መገለጫ መቁጠራቸው
  • ለራሳቸው ተከታይ ምዕመናን የክርስትና ትምህርትን እንዲያስፋፉ ጥሪ በማቅረብና ህዝበ ኦርቶዶክሱ ሃይማኖቱን በማስፋፋቱ በኩል በንቃት ባለመሳተፋ ወቀሳ ሲያቀርቡ ፥ በሙስሊሞች በኩል ያለዉን በተመለከተ መድረሳዎችን እና የቁርዓን ት/ቤቶችን የሚያስፋፉት አክራሪዎች ናቸው በማለት ወንጅለዋል
  • በመላው የሃገራችን ግዛቶች (ክልሎች) በኢስላማዊ ትምህርት በዲግሪ የሚያስመርቅ አንድም ተቋም የሌለ ሲሆን በዲፕሎም ደረጃ አንድ አወልያ ብቻ እንዳለ እየታወቀ አክራሪ ሙስሊሞች በነዚህ ዘርፎች ብልጫ ለማግኘት እየተንቀሳቀሱ በመሆናቸው ልናጋልጣቸው ይገባል ሲሉ ለምእመኖቻቸው ጥሪ አድርገዋል። ይህ አባባላቸው እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን በሃገራችን ያለንን መብት ለመንፈግ የተደረገ የማን አለብኝነት ስሜት ነው።

”ሽብርተኞቹ ንግድ እና ትምህርትን ቀላቅለው የሚያስኬዱ በመሆኑ መረጃ በመሰብሰብ እና በማጋለጥ ለመንግስት ማሳወቅ ይኖርብናል” ብለዋል። ይህም አባባላቸው ተምረው ራሳቸዉን ፣ ሃገራቸውን እና ህዝባቸውን ለማገልገል የሚተጉ ሙስሊም ዜጎችን ለማሸማቀቅ ብሎም ከትምህርት እና ንብረትን ከማፍራት ለመግታት የሚደረግ ኢ-ፍትሃዊ እና ኢ-ህገመንግስታዊ የዜግነት መብት ጥሰት ነው።

ዲያቆን ዳንኤል እንደ  አንድ የሃይማኖት አባት እውነት  በመናገር እና ሚዛናዊ ግምገማ በማድረግ  አርአያ ሊሆኑ  ሲገባ በተቃራኒው የእስልምናን ገጽታ  ለማጠልሸት ባላቸው ስሜት በመነዳት በክርስትናም ሆነ በሌሎች ሃይማኖቶች መሃል ግጭቶች የተነሱና ደም ያፋሰሱ እንደ ነበር በመሸሸግ  በእስልምና ውስጥ ብቻ ተነሱ የተባሉትን በማጋነን እኛ ሙስሊሞችን ለማሸማቅቅ ሞክረዋል ። እስልምና ከጥንት ጀምሮ ነውጥ ያስከተለ  ብቸኛ እምነት ለማስመሰልም

  • ሰለፍይ ብለው የሚጠሯቸውን ሲገልፁ -”ጥንት ከጅምሩ የአስተምሮቱ ተከታዮች እስልምናን ከቁርዓንና ከሃዲስ ውጭ ሌላ ጭማሪ ሳይደረግበት መተግበር አለበት የሚለውን ፅንሰ-ሃሳብ የሚያራምዱ  ናቸው “በማለት የኮነኑ ሲሆን፣ በተመሳሳይ አካሄድ በክርስትና እምነት   ውስጥ የ reformation  መሪና የፕሮቴስታንት ዘርፍ  መስራች የሆኑት ማርቲን ሉተርን  መፅሃፍ ቅዱስ ብቻ (sola scriptura)  ማለትም መፅሃፍ ቅዱስ ብቻ የእምነት መመሪያ ሊሆን ይገባዋል በሚል መርህ የፕሮቴስታንት የእምነት ዘርፍን   የመስረቱ መሆናቸውን ሸሽገዋል።
  • የስለፎች እንቅስቃሴ በአረቢያ እና አካባቢዋ በርካታ ግጭቶችን ያስነሳና ለበርካታ ህይወት መጥፋት ምክኒያት እንደ ነበረ ሲገልጹ እንደ አንድ ታአማኒነት ያለው እዉነት ፈላጊ የሃይማኖት አባት በማነጻጸር ሚዛናው ግንዛቤ እንዲኖረን በሪፎርሜሽን ሳቢያ ተቀስቅሶ  አውሮፓን ለ 124 አመታት (ከ 1524 እስከ 1648) የጦርነት አውድማ ያደረገዉንና የጀርመንን  ፣ የፈረንሳይን ፣የኦስትሪያን ፣የሃንጋሪን፣የጣሊያንን ፣የፖላንድን ፣ የስሎቫኪያ እና የዩክሬንን 30% ህዝቦች ለእልቂት የዳረገዉን አሰቃቂ ሃይማኖታዊ(ክርስትያናዊ)ጦርነትን ግን ለምን ሸሸጉን ? ሰለፎች   ባራመዱት አስተምህሮት ሳቢያ የተፈጠሩትን  የህይወትና የንብረት ውድመትን የምያሳዩ ማስረጃዎችን ቢፈትሹ እርሳቸዉም በስሜት ከመነዳት ድነው ሌሎች ወገኖቻችንንም ከስህተት እንዲድኑ ለማድረግ ይችሉ  ነበር።

ጥንትም ሆነ ዛሬ የጥፋት ሃይሎች በሁሉም ሃይማኖቶች ስም ወንጀል የሚፈጽሙ መሆናቸው እየታወቀ ዲያቆን ዳንኤል  ግን ለጥፋት የተሰማሩ ድርጅቶች በእስልምና ስም ብቻ የሚንቀሳቀሱ ለማስመሰል  እንደ አል ቃእዳ ፣ አል ሸባብ ፣ ቦኮ ሃራም ወዘተ ያሉትን የጥፋት ሃይሎች ብቻ ገልጸው በክርስትና ስም ጥፋት ያደረሱና በማድረስ ላይ ያሉትን  በሰሜን ዩጋንዳ በክርስትና ስም የምንቀሳቀሰዉን ፣ አስርቱን ቃላት በስራ የማዋል አላማ አለኝ የሚለዉን እና  እስከ 150 000 ለሚደርስ ህይዎት መጥፋት ምክኒያት የሆነዉን Lord Resistace Army LRA፣ በኦርቶዶክስ ስም ተንቀሳቅሰው በስረብረኒካ እስ 8 000 የሚደርሱ ሰላማዊ ሙስሊሞችን የፈጁ አክራሪ ኦርቶዶክስ ሰርቦች ፣ በ 2014 Central Africa በብዙ ሺ የምቆጠሩ ሙስልሞችን በግፍ የጨፈጨፉና የጥቂቶቹን ስጋ  የበሉ ራሳቸውን የክርስቲያን ሚሊሺያ ብለው የጠሩትንና ሌሎችንም   ሸሽገዋል።

በጥቅሉ የዲያቆን ዳንኤል ፅሁፍና አዉድዬ የአንድ ሃገር ዜጋ የሆነ ህብረተሰብን የዜግነት መብት የሚያስተባብል በእምነት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን እርስ በእርስ በባላንጣነት እንዲተያዩ በማድረግ ለጋራ ጥቅም እና መብት በጋራ እንዳይነሱ ለማድረግ ያለመ ነው።  እንደሃይማኖት አባትነት ወደ ልዩነት ከሚያመሩ ጎዳናዎች ምእመናንን በመከላከል ህዝቦች ተሳስበው ፣ ተከባብረው ፣ ልዩነቶቻቸውን አቻችለው እንድኖሩ መምከር ስጠበቅባቸው ፣ እሳቸው ግን በተቃራኒው ህዝባችን ተራርቆ ወገኖቻችን የጋራ ሃገራቸውን እንዳይጠብቁ እና እንዳይገነቡ እሳት የመጫር ዓላማ ያነገቡ ናቸው ለማለት እደፍራለሁ።

ጨረስኩ ።

ቸር እንሰንብት!

አብዱላህ

25 March 2015

The post የዲያቆን ዳንኤል ስሜታዊ ትንታኔና መሬት ላይ ያለው እዉነታ ! የመጨረሻ ክፍል – አብዱላህ appeared first on Zehabesha Amharic.

ጊፍት ሪል እስቴት ወደፊት ወይስ ወደ ኋላ

$
0
0

nlmqi6fn76e6fjt0pj5uአንዳንዴ እንዳለመታደል ነው መሰል በሌሎች ሀገሮች ተብለው ተብለው ያለቀላቸው ነገሮች እኛ ሀገር ሲገቡ ልክ በዓለም ለመጀመሪያ ጊዜ እንደምንሠራቸው መስለው ቁጭ ይላሉ፡፡ ሌላ ቦታ ተሠርተው፣ ችግሮቻቸው ታውቀው፣ ልምድ ተቀስሞባቸው፣ አዳዲስ አሠራሮችና ቴክኖሎጂዎች ተፈልስፈውላቸው፣ የኖሩ ጥበቦች እኛ ሀገር ሲገቡ የእናታቸው መቀነት ያደናቅፋቸዋል፡፡ እንዲህ እንድል ከሚያደርጉኝ ነገሮች አንዱ ሪል እስቴት ነው፡፡ ከምዕተ ዓመታት በላይ የዘለቀን የቤቶች ግንባታ ዘዴ እኛ ሀገር ገብቶ መከራውን ሲያይ መታዘቤ ነው እንዲህ ያሰኘኝ፡፡ በሰው መሬት ላይ መገንባት፣ ያልተገባ ውል ከቤት ገዥ ጋር መዋዋል፣ ለአካባቢ ጤናና ውበት አለመጨነቅ፣ በጊዜ ገንብቶ አለማስረከብ፣ ገንዘብን ይዞ ከሀገር መጥፋት፣ ቤት እሠራለሁ ብሎ የወሰዱትን መሬት መሸጥ፣ የፍሳሽ ማስወገጃና የውስጥ ለውስጥ መንገድ የሌለው መንደር መገንባት፣ ኧረ ስቱ ይነገራል፡፡

እኔ ጊፍት ሪል እስቴት ከሚባል ድርጅት የዛሬ ሰባት ዓመት ቤት ገዝቻለሁ፡፡ የቤቱን ዋጋ በመቶ በመቶ ከፍያለሁ፡፡ መቶ በመቶ ብትከፍሉ በፍጥነት ይደርስላችኋል ዋጋም ይቀነስላችኋል ተብሎ ስለነበር፡፡ ጽድቁ ቀርቶ በወጉ በኮነነኝ አሉ፡፡ ነገር ግን ይሄው ሰባት ዓመት ሆነው፤ ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም ሆኗል፡፡ የቤቱ መሠረት ከመውጣት ያለፈ ነገር ጠብ ሊል አልቻለም፡፡ በተደጋጋሚ ከዋና ባለቤቱና ሥራ አስኪያጁ ጋር ተነጋግረናል፣ ከአራት ጊዜ በላይ ተጻጽፈናል፡፡ ውጤት ግን አላመጣም፡፡

ጊፍት ከደንበኞቹ ጋር ውል ሲፈርም በአሥራ ስምንት ወራት ገንብቶ ሊያስረክብ ነበር ግዴታ የገባው፡; እኔ እስከማውቀው ድረስ ግን ከሦስት ዓመት በፊት ገንብቶ ያስረከበው ቤት የለም፡፡ ገንብቶ ያስረከባቸው ቤቶች ቢሆኑም አምስት ችግሮች አሉባቸው፡፡ የመጀመሪያው የባለቤትነት ማረጋገጫ የላቸውም፡፡ ጊፍት ሪል እስቴት ስሙ እንዲነሣበት ከማይፈልጋቸው ነገሮች አንዱ የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ነው፡፡  የአዲስ አበባ መስተዳድር እንኳን ሕገ ወጥ ይዞታዎችን ሕጋዊ ለማድረግና ካርታ ለመስጠት በተዘጋጀበት በዚህ ዘመን ጊፍት ግን ቤት ላስረከባቸው ሕጋዊ ገዥዎች እንኳን የባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተሩን ለመስጠት ፈቃደኛ አይደለም፡፡ ሲጠየቅም የየካ ክፍለ ከተማና የአዲስ አበባ መስተዳድር ካርታውን እንደያዙበትና ለማስለቀቅ እየታገለ መሆኑን ነው የሚናገረው፡፡ ምንጊዜም የሚያመካኘው በመስተዳድሩ ነው፡፡

ሁለተኛው ችግራቸው መንገድ ነው፡፡ ወደ ጊፍት ሪል እስቴት የሚወስደው መንገድ በሁለት ችግሮች ምክንያት አልተሠራም፡፡ አንደኛው ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በተፈጠረ ግጭት ሲሆን ሌላው በሪል እስቴቱ ድክመት፡፡ ድርጅቱ ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር አይጥና ድመት ሆኖ  ነው የሚኖረው፡፡ ለዚህ አንደኛው ምክንያት ደግሞ ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ከመፍታት ይልቅ ማስፈራራትን ስለሚመርጥ ነው፡፡ የክፍለ ከተማው ባለሥልጣናት ባሉበት ችግሩን ለመፍታት የተጠራውን ስብሰባ የጊፍት ኃላፊዎች ባለመገኘታቸው ነው ውጤት አልባ የሆነው፡፡ የድርጅቱ መኪኖችም ሆኑ ነዋሪዎቹ ከዋናው አስፓልት ወደ ግቢው ለመግባት የሚጠቀሙበትና ‹መሪ ቁጥር አንድ› የሚባለው መንገድ ጊፍት ሪል እስቴት የሚደርስበትን መዋጮ ባለመክፈሉ ከሁሉም የአካባቢው መንገዶች ተለይቶ እስካሁን አልተሠራም፡፡ አስፓልት ይሆናል የተባለው መንገድ ኮብል ስቶን እንደናፈቀው ቀርቷል፡፡ የወረዳው መስተዳድር ችግሮቹን ለመፍታት ያደረገው ጥረትም በድርጅቱ እምቢ ባይነት ከሽፏል፡፡ ክፍለ ከተማውም ከዐቅሜ በላይ ነው ብሏል፡፡ ነዋሪዎቹ ግን ይሰቃያሉ፡፡

በሪል እስቴቱ ግቢ ውስጥ መንገድ የለም ማለት ይቻላል፡፡ በተፈጥሮው ሜዳ የሆነ ነገር እንጂ ሆነ ተብሎ የተሠራ መንገድ የለም፡፡ ከቤት ገዥዎቹ ጋር በገባው ውል መሠረት ግን የውስጥ ለውስጥ መንገዶችን ሠርቶ የማስረከብ ግዴታ ነበረበት፡፡ በግቢው ውስጥ ያሉ ኃላፊዎች ድርጅቱ ገንዘብ ስለሌለው ሊሠራው እንደማይችል ይነግሩናል፡፡ ዘወትር የሚሰጡት ምክንያት የነዳጅ ብር ስለጠፋ፣ መካኒኩ ደመወዝ ስላልተከፈለው፣ የሠራተኞች ደመወዝ ስላልደረሰ፣ መኪናው ተበላሽቶ የመለዋወጫ መግዣ ስለሌለ የሚል ነው፡፡ ያ ግን ሕጋዊ ምክንያት ሊሆን አይችልም፡፡ ወይ ባልዘፈንሽ እንደሚባለው አሁን መሐል መንገድ ላይ ዐቅም የለኝም ከማለት መዘጋጀት አስቀድሞ ነበር፡፡ ዝናብ ጣል ካደረገ ጊፍት ግቢ ውስጥ በቦቴ ጫማ እንኳን ለመግባት ከባድ ነው፡፡ መግባት የሚቻለው በሄሊኮፕተር ብቻ ነው፡፡ ለዚያውም ማረፊያ ከተገኘ፡፡

ሦስተኛው ችግር ውኃ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ነዋሪ ወር ሙሉ ውኃ ጠፋብኝ ብሎ ያማርራል፡፡ ጊፍት ግቢ ውስጥ ግን ላለፉት ሰባት ዓመታት ውኃ የለም፡፡  ውኃ በአህያ እያሸከሙ ቤት የሚሠሩ የሪል እስቴት ባለቤቶች ያሉት ጊፍት ግቢ ነው፡፡ ውኃ የሌላቸው የአራት ሚሊዮን ብር ቤት ሠሪዎች ያሉት ጊፍት ግቢ ነው፡፡ አንዳንዶች ከአካባቢው በጀሪካል እየገዙ፣ ሌሎች በቦቴ እያስመጡ፣ ሌሎች ደግሞ በአህያ እያጓጓዙ ነው ኑሮን የሚገፉት፡፡ ውኃ የሌለው ብቸኛው የሀገራችን ሪል እስቴት ነው ጊፍት፡፡ በዚህ አያበቃም አራተኛ ችግርም አለ፡፡ ጊፍት ውስጥ መብራት የለም፡፡ ለነዋሪዎቹ የታደለቺው መብራት የፍሪጅ መብራት ናት፡፡ ቤቱ ውስጥ መብራት መኖሩን ከመናገር ያለፈ ሌላ ትርጉም የሌላት፡፡ ሰሞኑን የሚደረገውን የምርጫ ክርክር በቴሌቭዥን የማያዩ ነዋሪዎች ያሉት ጊፍት ግቢ ነው፡፡ የኤሌክትሪኩ ኃይል ቴሌ ቭዥን አያንቀሳቅስም፡፡ እንጀራ መጋገርና ስቶቭ መጠቀምማ ጎረቤት ላለው ሥላሴ ተሥለውም አያገኙት፡፡ እንደ ራሽን ጊፍት አንድ ቆጣሪ ለስድስትና ለሰባት አከፋፍሏቸዋል፡፡  አምስተኛው ችግር ደግሞ የፍሳሽ ማስወገጃው ነው፡፡ ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በተፈጠረ ግጭት የግቢው የፍሳሽ ማስወገጃ አልተሠራም፡፡ ማጠራቀሚያ ተብሎ ግቢው ውስጥ የተሠራው ዋና ጉድጓድም ከመፋሰሻው ጋር አልተገናኘም፡፡ ለዚያውም የሰዎች ቤት በር ላይ የተሠራ አስገራሚ ዲዛይን ያለው የማጠራቀሚያ ጉድጓድ ነው፡፡

እነዚህን ችግሮች እንዲፈታ፣ መንደሩን ወደ መኖሪያነት እንዲቀይር ድርጅቱ በተደጋጋሚ በደንበኞቹ ተነግሮታል፡፡ የመፍትሔ አቅጣጫዎቹ ግን አስደናቂ ናቸው፡፡ አንዳንድ ጊዜ የሐሰት ቃል ይሰጣሉ፡፡ የዛሬ ወር፣ የዛሬ ሳምት፣ ከሦስት ወር በኋላ ያልቃል ይላሉ፡፡ ለእነርሱ ሳምንትም፣ ወርም፣ እኩል ናቸው፡፡ አንሠራም ማለት ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ አብዛኞቹ ገዥዎች ውጭ ሀገር ስላሉ ለጊዜው ጩኸው ይሄዳሉ ብለው ያምናሉ፡፤ ስለዚህም ቢሯቸውን ዘግተው ይጠፋሉ፡፡ የሉም፣ ስብሰባ ላይ ናቸው፣ ውጭ ሀገር ሄደዋል የጸሐፊዎቹ መልሶች ናቸው፡፡ ከዚህ የባሰ ከመጣ ደግሞ በክፍለ ከተማውና በከተማው መስተዳድር ያመካኛሉ፡፡ ክፍለ ከተማው አስቸገረን፣ መስተዳድሩ የኛን ጥያቄ አይመልስም፣ ወዘተ የተለመዱ ማመካኛዎች ናቸው፡፡

እንዲህ እየሆነ ግን እስከ መቼ መጓዝ ይቻላል? ባፉት ሰባት ዓመታት ከሰባት በላይ የሥራ ኃላፊዎች ተቀያይረዋል፤መፍትሔ ግን አልመጣም፡፡ እንደ ከበደ ሚካኤል ግጥም የሰማው ሲሄድ ያልሰማው ይመጣል፡፡ ድርጅቱ ኮርፖሬት ኃላፊነቴን እየተወጣሁ ነው ብሎ ለቀይ መስቀል ቤት ሲሰጥ መስቀል አደባባይ ላይ ቢል ቦርድ ለጥፏል፡፡ የኛን ቤት ግን እስካሁን አላስረከበም፡፡ አሁንም በዓል በመጣ ቁጥር ቤት አስረክበናል፣ ሌሎቻችሁ ግዙ ይላል፡፡ በሚገባ ያስረከበው ቤት ግን የለም፡፡ ይኼ ሁኔታ የሚያዛልቅ አይመስለኝም፡፡

  1. ድርጅቱ ዐቅም ከሌለውና ቃሉን የማያሟላ ከሆነ የውሸት ቃል በየጊዜው ከሚገባ ቁርጡን ይንገረን
  2. የሚመካኝባቸው የመንግሥት አካላትም ጠርተው ይጠይቁት
  3. ቃሉን እንዳላሟላ እያወቁ አሁንም ሌሎች ደንበኞችን የሚሸነግሉ አስተዋዋቂ ድርጅቶችም የሞራል ኃላፊነታቸውን ይወጡ
  4. ቤት ገዥዎችም ከመንገብገብና ቢሮ እየሄዱ ከመጨቃጨቅ ይልቅ እንደ አክሰስና በርታ ቤት ገዥዎች ተደራጅተው የጋራ መፍትሔ ይስጡ

 

 

 

 

The post ጊፍት ሪል እስቴት ወደፊት ወይስ ወደ ኋላ appeared first on Zehabesha Amharic.

ለምወደው እና ለማከብረው ሕዝብ እውነትን የሚገልጽ ውሃን የሚተፋ እንጂ እሳትን የሚተፋ ብዕር የለኝም።

$
0
0

ለአቶ መሃመድ ሙፍታህ -ከተማ ዋቅጅራ

በምስጋና እና በማሳሰቢያ ልጀምር።

Ketemaዘሐበሻ ላመሰግናችሁ እፈልጋለው ምክንያቱም የሚዲያ ተግባርን ስራ በአግባቡ እየተወጣችሁ እንዳለ ይሰማኛል። ከግራ ከቀኝ ያለውን ነገር ያለ አድሎ አቅርባችሁ ህዝብ እንዲያየው እና አስተያየቱን እንዲሰጡ ስላደረጋችሁ ለናንተ ትልቅ ቦታ እንዲኖረኝ አድርጎአል። በሚዲያችሁ የሚሰጠውን ትችት ዋጋ ቢስ እንደሆነ ያሳወቃችሁበት እና ነጻ ሚዲያን ለማይፈልጉት አፋኞች ለሚሰጡት ትችት በሙሉ መልስ የሆናችሁ ስለሆነ ምስጋናዬ ላቅ ያለ ነው። በመቀጠልም መሃመድ ሙፍቲህ ስለሰጠኸው የግል አሳብህ ላመሰግንህ እወዳለው። ምክንያቱም ሁሉም ነገር ወደ እውነት ወደሚነገርበት እና ህዝብ ፍርድን ወደሚሰጠው ወደትክክለኛው ሃሳብን በብዕር በመግለጽ ያልተማረው እንዲማር ያላወቀው እንዲያውቀው የማድረጉን ውይይት መምጣቶ ተገቢ ነው። ብዕር ብዙሃኑን የሚያሳውቅ፣ ብዕር ብዙሃኑን የሚያነቃ፣ ብዕር ብዙሃኑን እውቀትን የሚያስጨብጥ፣ የአለማችን የጥበብ ገላጭ ናት። አቶ መሃመድ ሙፍታን ሰለ አስተያየቶት ክብር አለኝ። ነጻነት ማለት ይሄ ነው። የኔም ሃሳብ ወደዚህ ነጻነት  እድንመጣ እና ሃሳባችንን እንድንገልጽ ነው። ሌሎችም የሙስሊም ሙሁሮች በእስላም ስም የሚደረገውን እንቅስቃሴ እስልምናን እንደማይወክሉ እንደዚህ ወተው ማስተማር ከቻሉ ድል ማለት ይሄ ነው።

ማሳሰቢያው ደግሞ አስተያየት ለምትሰጡ ሰዎች። አስተያየት ሰጪ ሶስት አይነት ሰዎች አሉ

1ኛ. በትክክል ጽሁፉን አንብቦ የራሱን ሃሳብ የድጋፍም ይሁን  የትችታዊ ሃሳብ ያቀርባሉ። እንደነዚህ አይነት አስተያየት ሰጪዎች እራሳቸውን ለውይይት በሰለጠነ መንገድ የሚያቀርቡ መጥፎንም ጥሩንም ተችተው የሚያልፉ ናቸው። እንደነዚህ አይነቱ አስተያየት ሰጪ ጥሩ አመለከካከት ያላቸው ናቸው።

2ኛ.ጭፍን ጥላቻ ያላቸው ሰዎች የሚሰጡት አስተያየት ነው።  እንደነዚህ አይነቱ የራሳቸውን ሃሳብ ብቻ በየትኛውም አቅጣጫ መስማት እና ትክክል እንደሆነ እንዲነገርላቸው አልያም እንድታሰማቸው የሚፈልጉ ናቸው። ወይ ማስረዳት የማይችሉ ወይ መረዳት የማይፈልጉ ሲሆኑ። እንደነዚህ አይነት ሰዎች ለደጋፊም ለተቃዋሚም አይሆኑም።

3ኛ. ወያኔ ሆን ብሎ  ለዚህ አላማ ያሰማራቸው ሰዎች አሉ። እነዚህ ሰዎች ከ3-5 በክርስቲያን ስም ከ3-5 በእስላም ስም ከ3-5 በኦሮሞ ስም ከ3-5 በአማራ ስም ከ3-5 በትግሬ ስም እያለ ይቀጥላል። እንደነዚህ አይነት ሰዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ለዚህ ስራ አንዱ ከአንዱ እንዲጋጭ በመንግስት ከፍተኛ ብር የሚከፈላቸው እና የነጻ ሚዲያን የማንቋሸሽ ስራ የሚሰሩ ካድሬዎች አሉ። እነዚንም የመሳሰሉትን ከግምት ውስጥ በመክተት ነገሮችን ከተለያየ አቅጣጫ እንደሚመጡ መረዳት ተገቢ ነው።

ወደ ቁምነገሩ ስገባ ኢትዮጵያ ክርስቲያን፣ እስላም፣ ዋቄፈና፣ ደብተራውም፣ ጠንቋዩም እምነት የሌለውም በህብረት የሚኖሩባት አገር ናት። እኔ መግለጽ የፈለኩት ግን አቶ መሃመድ የተረዱት አይመስለኝም። ምክንያቱም ለዚህ ጥቃት ኢትዮጵያ ውስጥ በሚፈጠረው የፖለቲካ እንቅስቃሴ መሃል ኢራቅ፣ ሶሪያ፣ ሊቢያ፣ የመን፣ የመሳሰሉት የአገራቸው ፖለቲካ ለውጥ ለማምጣት በሚደረገው እንቅስቃሴ የራሱን ሃይል አደራጅተው ታላቅ ጥፋት ያደረሱት እዚህ ጋር አሜሪካ ናት ወይም እስራኤል ናቸው የፈጠሩአቸው  የሚለውን ትንታኔ ውስጥ አልገባሁም መግባትም አልፈልግም እሱ እራሱን የቻለ ሰፊ ጥናት እና ሰፊ ገለጻ የሚያስፈልገው ጉዳይ ነው። ዋናው ጉዳይ በነዚህ አገራት ውስጥ የተፈጠረው ችግር በውስጥ የፖለቲካ መቃወስ ምክንያት ነው። የኔም ስጋት እነዚህ ሃይሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካው እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ  ወደ መለውጡ ሁኔታ እያመራ እና  የተወጣጠረ ነገር ስላለ ለሰላማዊው ህዝብ ለክርስትናውም ለሙስሊሙም ለሁሉም… ከሩቅ ያየነው ቤታችን እንዳይገባ ቀድሞ ለፖለቲከኖች እና ለህዝቡ ግንዛቤን መስጠቴ በኢትዮጵያ ሙስሊም በሙሉ የተደረገ ጥቃት አድርገህ ማቅረብህ ስህተት ነው። የግሎን ሃሳብ የሁሉም ሙስሊም አድርገው ማቅረብ በራሱ ከስህተ ሁሉ የከፋ ስህተት ነው። ጽሁፎን ሊደግፉ የሚችሉትን ያህል ያን ያህል አልያም እጥፍ ሊሆን የሚችሉ አንባቢም ሊቃወሞት እንደሚችሉ መገንዘብ ይኖሩቦታል። የርሶን ጽሁፍ መነሻ አድርጌ በሌሎች አማኒያን ላይ የተቃጣ ጽሁፍ ብዬ ላቀርብ በየትኛውም አቅጣጫ ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ እና ኢፍትሃዊ ነው። እዚህ ጋር የተገነዘብኩት እርሶ  መስማት የሚፈልጉት ብቻ መስማት የሚፈልጉ አልያም እንዲነገርሎ የሚፈልጉትን  ብቻ እንዲነገርሎ የሚፈልጉ ሰው መሆኖን ነው።

አቶ መሃመድ ትንሽ ወደኋላ ሄደውም ታሪክን ለመጥቀስ ሞክረው ነበረ። አጼ ዮሐንስ እስላሙን ህብረተሰብን ጨፍጭፈዋል ብለውን ነበረ። ይህ የሚወገዝ ጉዳይ ነው። እኔም አወግዘዋለው። ከፖለቲካው አለም ወጥተው  ሃይማኖታዊ ክርክር  አስመሰለቦት። እዚህ ጋር ግን እርሶ ትክክለኛ ሰው ቢሆኑ ኖሮ ግራኝ መሃመድ በክርስቲያኖች ላይ ያደረሰውንም ጭፍጨፋ  ጠቅሰው ማለፍ ሲኖርብዎ እርሶ ግን የራስህን ስሜት ብቻ እንጂ እውነትን ሊነግሩን ያለመፍቀዶ ለምን ይሆን?። አቶ መሃመድ ሚዛናዊ የሆነ ንግግር እና  እውነተኝነትን የተላበሰ ነገሮችን ማቅረቡ ተገቢ ነው። ተድበስብሶ የሚታለፍ ነገሮች በሙሉ በውስጡ የተደበቁ ነገር እንዳሉ የሚያሳዩ ናቸው።

ጽሁፌንም ከድምጻችን ይሰማ ጋር አገናኝተውታል። ይሄ ደግሞ ሌላው የስህተት እራስ ነው። እኔ ድምጻችን ይሰማ ላይ ምንም ተቃውሞ የለኝም። የኔም አስተያየት ድምጻቸው ይሰማ ነው። ወያኔ የሙስሊሙን ህብረተሰብ ሃይማኖት ውስጥ ገብቶ ድምጻቸውን አፍኗል። ለዚህ የመብት ጥያቄ የኔም ጥያቄ ነው። በዚህ አጋጣሚ የሙስሊሙን ድምጽ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያሰሙ ሃጂ ነጂብ መሃመድ እንዲሁም ዑስታዝ ካሊድ ዑመር እና ጋዜጠኛ ሳዲቅ መሃመድን  ከልቤ የማደንቃቸው እና በመነጋገር የሚያምኑ የሁሉንም ድምጽ የሚሰሙ የራሳቸውንም ድምጽ የሚያሰሙ እና በማስተዋል የሚጓዙ አገላለጻቸውን ጭምር የማከብርላቸው ሙስሊም ወንድሞቼ ናቸው። እዚህ ጋር ሊሰመርበት የሚገባው ክርስቲያን ሁሉ ቅዱስ ነው ማለት አንችልም ክርስቲያን ሆኖ ክፋትን የሚያራምድ አለና ስለዚህ ይህንን ክፋትን የሚያራምደውን ግለሰብ ክርስቲያን ስለሆነ  ብቻ የሚሰራውን የጥፋት ስራ ልንደብቅለት ወይም ልንደባብስለት አይገባም። ሙስሊሙ  ውስጥም ሁሉም ቅዱስ አይደሉም ከመሃል ክፋትን የሚያራምድ አለና ስለዚህ ይሄንን ክፋትን የሚያራምደውን ግለሰብ እስላም ስለሆነ ብቻ መጥፎ ስራውን ልንደባብስለት አይገባም። ለክፋት አራማጆች የምንደብቅላቸው አልያም የምደባብስላቸው ከሆነ ግን አደጋ አለው ነው የኔ  ሃሳብ። እንደ ዜጋ በቅን ልቦና ያሰብኩትና ያስቀመጥኩት ቁም ነገር ይሄ ሆኖ ሳለ በኢትዮጵያ ሙስሊም ህብረተሰብ የተቃጣ እሳታዊ ብዕር አይደለም። እንዲህም እንዳላሰብኩ  አንባቢው ከጽሁፌ ሊረዳ ይችላል። ለአስረጅነት ከጽሁፌ ጋር አያይዤ የማቀርባቸው ሊንኮችን አይተው መልሶትን እንደሚሰጡኝ ተስፋ አደርጋለው? እኔ ካለመረጃ አይደልም የምናገረው ከመረጃ ጋር ነው እርሶም መረጃዎችን ማቅረብ ቢችሉ ጽሁፎ ተቀባይነት ሊኖረው ይችላል።በጽሁፎ ርዕስ ላይ እንደገለጹት ፍራቻ እንዳለኝ እና በመሃልም ላይ ዋጋ እንደምከፍል ነግረውኛል። እዚህ ጋር እንዲያውቁት የምፈልገው ስለ እውነት ማንኛውንም ነገር የመቀበል ጉጉት እንጂ ፍራቻ የለኝም። ክርስትና ውስጥ ፍራቻ የሚባል ነገር የለም። ከፈራ እርሱ እምነት የጎደለው ነው። ስጋን የሚገሉትን አትፍሩ ነገር ግን ስጋንም ነፍስንም በአንድ ላያጠፋ የሚችለውን  እግዚአብሔርን ፍሩ ይላ መጽሐፍ ቅዱስ። ስጋን የሚገድሉትን ቅንጣት ያህል እንደማልፈራ እና እውነትን ይዜ የምጓዝ ክርስቲያን ነኝ። በሐይማኖቴ የሚመጣውን መከራ በሙሉ በደስታ ነው የምቀበለው ነገር ግን ክርስትናን በግድ ተቀበሉ ብዬ በሌሎች ላይ  መከራ መጫን ግን አልችልም። እምነት የግል ስለሆነ ክፉም ቢሰራ ደግም ቢያደርግ ዋጋን ከፋዩ እግዚአብሔር  ስለሆነ ፍርድን ለእግዚአብሔር እንተው።

አቶ መሃመድ ISISን እርሶ እንደሚቃወሙት እና እስላምን እንደማይወክል ነግረውናል። ይሄ ያስማማናል የጋራ ጠላታችን ስለሆነ አብረን እንመክተዋለን። ይሄ ትክክለኛ ሃሳብ ነው። ወደፊትም እንደዚህ ISIS ስህተተና እንደሆነ እና አረመኔአዊ እንቅስቃሴ እንደሚያደርግ እያስተማሩ ቢቀጥሉ እና ብንሰማ  ደስተኛ ሆነን ተደጋግፈን እንጓዛለን። ነገር ግን ይህ አልሆነም ዝምታው በዝቷል። ይሄ አደጋው ደግሞ  ለሁሉም ዜጋ ነው። የኢትዮጵያም ፖለቲካ ሁኔታ አስጊ ደረጃ ላይ ነው። ትግሉ ስለበረታ በዚህ መሃል አደጋ አገራችን ላይ እንዳይመጣ  ክርስቲያኖችም እስላሞችም ዋቄፈናም ይሁዲዎችም ፖለቲከኞችም ጥንቃቄ ማድረግ አለብን ማለቴ እስላምን ታርጌት ያደረገ ሊባል ባልተገባ ነበረ። እዚህ ጋር የጸሃፊውን ዝቅ ያለ የአስተሳሰባዊ እይታ እንዳለው እመለከታለው።

በመጨረሻም ላስተላልፈው የምፈልገው ነገር ሁሉም ሃይማኖት ውስጥ ሊታይ የሚገባው ሰው በሰውነቱ ብቻ ሊከበር ይገባዋል። የአንዱን እምነት ካልተቀበልክ ብለን ሊጫንበት የሚገባ ግዴታ  መቀመጥ አምላክ የማይፈቅደው ነው። ነገር ግን ሙስሊም ትክክለኛ እምነት ነው ብሎ ማስተማር ይችላል አስተምሮም  ወደ እስልምና ሊቀይር ይችላል። ነገር ግን የተቀያሪው ቤተ- እምነት እምነቱን በቀየረው ላይ የሞት ፍርድ መፍረድ ግን በምድርም በሰማይም መንግስት ዋጋ ያስከፍላል። ክርስትና ትክክለኛ እምነት ነው ብሎ ማስተማር ይችላል አስተምሮም  ወደ ክርስትና ሊቀይር ይችላል። ነገር ግን የተቀያሪው ቤተ- እምነት እምነቱን በቀየረው ላይ የሞት ፍርድ መፍረድ ግን በምድርም በሰማይም መንግስት ዋጋ ያስከፍላል። ስለዚህ የግለሰቡ ሃሳብ ወደፈለገበት አምኖ  በሚንቀሳቀስበት ግዜ መብቱ ሊከበርለት ይገባል ነጻነት ማለት ይሄ ነው። ሁሉም ሰው እራሱን ይወዳል  በራሱ ውስጥ ደግሞ  የሚያምነው አምላክ አለ። የሰውየውን የግሉን እምነት ልንተች እንችል ይሆናል ትክክልም  አይደለህም ልንለው እንችላለን። ነገር ግን የኛን እምነት ካላመንክ መጥፋት አለብህ ማለት ግን አይቻልም።

ከዚህ ቀጥዬ የምልክሎትን ሊንኮች ተመልክተው ምላሾን እንደሚለግሱኝ ተስፋ አደርጋለው። ጥቂት ሙስሊሞች ለሚያነሱት ጥፋት ፈጥነው ከእስላም ወንድሞቻችን መልስ ቢሰጥባቸው እና ቢያወግዟቸው ብዙ ስራዋችን መስራት ይቻላል። እኔም ያየሁትንና የሰማሁትን የማውቀውን ጽፌአለው።ጽሁፌም ለነጻነት ለፍትህ የሚታገሉትን ሙስሊም ደግፌ እንደሆነ ሊሰመርበት ይገባል። ከእስላም እህት እና ወንድሞች ጋር አብሬ ተጫውቼ በፍቅር ያደኩና አሁንም በፍቅር የምንጫወት እስላም ጓደኞች  አሉኝ። የኔ ፍራቻ እስላም ወጎኖቼ ሳይሆኑ በእስላም ስም ሰይፍ ይዘው የሚነሱትን ነው። አቶ መሃመድ ይህ ደግሞ  ስጋቱ ለእስላሙ ህብረተሰብ ጭምር ነው። ወይንም ደግሞ እርሶ ከዚህ የተለየ የውስጥ አጀንዳ ካሎት ጽሁፌ ላይስማማዎት ይችላል። ይሄንን ሊንክ ይመልከቱት http://www.independent.co.uk/voices/comment/iraq-crisis-how-saudi-arabia-helped-isis-take-over-the-north-of-the-country-9602312.html እነዚህ ጉሩፖች እንኳን ሌላ ሃይማኖት ላለው ይቅርና ለእስላሙ የማይተኙ ደም አፍሳሾች መሆናቸውን እየተመለከትን ነው። ስለዚህ እስላም ክርስቲያን ዋቄፈና ፖለቲከኞችም  አብረን እንታገላቸው። በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚመጣው አይቀሬ ለውጥ ምክንያት በሚፈጠረው ክፍተት እነዚህ ግሩፖች ወደአገራችን እንዳይገቡ ጥንቃቄ ማድረግ አለብን እንጂ ቸል ብለን ወይም ደባብሰን ለማለፍ መሞከራችን ከአደጋው አያስቀረንም ቅድሚያ ጥንቃቄ ካደረግን ግን በህብረት እንመክተዋለን የሚል ድምዳሜ ያለው ጽሁፌን አቶ መሃመድ  ወደ ሃይማኖታዊ ገጽታ ለውጠውት አጠቃላይ የኢትዮጵያ እስላም ላይ የተቃጣ ብለው ያቀረቡት ግን አንባቢው ብቻ ሳይሆን እርሶም ረጋ ብለው ጽሁፌን ከተረዱት ከኔ ጎን እንደሚሰለፉ ተስፋ አደርጋለው።  ነገር ግን የግሎት ሃሳብ ከሆነ እቀበላለው ።የሁሉም ሰው ሃሳብ የተለያየ ስለሆነ ። እስላሙን ሁሉ ወክለው ግን የተናገሩትን ንግግር ከምን አንጻር እንደሆነ ባይገባኝም ፍርዱን ለአንባቢ ትቼዋለው።

የተወሰኑ ጥያቄዎች ልጠይቆት እና  ሃሳቤን ልቋጭ

1ኛ ISIS የሚደግፉ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም የሉምን? ወደ አፍጋኒስታን ኢራቅ ቱርክ  የሚሄዱት አንድ አንድ ኢትዮጵያዊ ሙስሊሞችን  እንዴት ይመለከቷቸዋል? ኢትዮጵያ፣ ኤርትሪያ፣ ሱማሊያ፣ የሆኑ የሌላ አገር ዜግነት ኖሮአቸው ወደነዚህ ጉሩፖች መቀላቀላቸው ምንን ያመለክታል? ላገራቸው ነጻነት ነውን? BBC በቅርቡ የዘገበው ሶስት ከሃያ አመት በታች ያሉ የእንግሊዝ ዜግነት ያላቸው  ይሄንን ግሩፕ መቀላቀላቸውን ዘግቦ  ነበረ ከነዚህ ውስጥ አንዷ የአስራ ሰባት አመት የሆነች ሴት ኢትዮጵያዊ ሙስሊም እንደሆነች አሳይቶን ነበረ  በርሶ እይታ ይሄ ድርጊት ምንድንው? በዚህ አይነት እንቅስቃሴ የተሳተፉትን ዜጎች ህብረተሰቡ እንዲያውቃቸው መደረጉ አቶ  መሃመድ ለርሶ  ጠቅላላ ሙስሊምን ይወክላል ያስብላልን? የነዚህን እንቅስቃሴ ማጋለጥ ለምን ኢትዮጵያ ሙስሊም ላይ ሁሉ እንደተነገር አድርገው ማቅረብ ለምን ፈለጉ? ወይስ ይሄ እናንተን አይመለከትም ዝም በሉ ማለቶት ነው?

http://www.cbc.ca/news/world/shamima-begum-amira-abase-kadiza-sultana-what-we-know-about-isis-bound-teens-1.2967193

2ኛ. አያይዜ ያቀረብኩሎትን ሊንኮች  በኢትዮጵያ ላይ በአንድ አንድ አክራሪ እስላሞች የተደረጉ ድርጊቶች ናቸው። ስለዚህ ምን ይላሉ?  እንደዚህ አይነቱ እንቅስቃሴ ህብረተሰባችን ላይ ያደረሰውን ቀውስ ድርጊቱን ኮንነው እና አውግዘው አስተምረው ይሆን? ከሆነም በመረጃ አስደግፈው ቢያሳዩኝ?                                                                    https://www.youtube.com/watch?v=me1joZHo0Zohttps://www.youtube.com/watch?v=lemvyk5KCp8 ,                                               https://www.youtube.com/watch?v=aVm_AscRaRo

3ኛ. ISIS እስላሚክ ስቴት ብለው ባስቀመጡት አገራት ካርታ ላይ ምን አይነት አስተያየት አሎት?

https://www.google.no/search?q=ISIS+MAP&safe=active&biw=1366&bih=624&tbm=isch&tbo=u&source=univ&sa=X&ei=4R3uVMv-H6b-ygPZhYDYBQ&ved=0CBwQsAQ

አቶ መሃመድ ሙፍታህ ወደ  መድረኩ ስለመጡ እንዘህን ጥያቄ መልሰው ይውረዱ።

መጥፎን ድርጊቶችን ሁላችንም በህብረት እናውግዘውና  እንከላከለው እላለው።

ከተማ ዋቅጅራ                                                                                                                                     25.02.2015                                                                                                                                                            Email- waqjirak@yahoo.com

The post ለምወደው እና ለማከብረው ሕዝብ እውነትን የሚገልጽ ውሃን የሚተፋ እንጂ እሳትን የሚተፋ ብዕር የለኝም። appeared first on Zehabesha Amharic.

“በራስህ ላይ እራስህ ጥላቻን አትፍጠር”–የወጣት ቤዛ ኃይሉ መልዕክት (በድምጽ)

የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልዕክት ለ8ኛ ጊዜ ተመለሰ

$
0
0

• ኢብኮና የአዲስ አበባ አስተዳደር መገናኛ ኤጀንሲ የሰማያዊ ፓርቲን የቅስቀሳ መልዕክት መልሰዋል

• ‹‹አማራጫችን እንዳናቀርብ እየተከለከልን ነው›› አቶ ዮናታን ተስፋዬ

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እና የአዲስ አበባ አስተዳደር መገናኛ ኤጀንሲ የሰማያዊ ፓርቲን የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ‹‹አናስተላልፍም›› ብለው መመለሳቸውን ድርጅቶቹ ለፓርቲው በላኳቸው ደብዳቤዎች ገልጸዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ መጋቢት 16/2007 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የብሔራዊ ራዲዮ በአማርኛ ስርጭት የሚተላለፍ ‹‹መንግስታዊ አወቃቀር›› የሚል የቅስቀሳ መልዕክት ልኮ የነበር ሲሆን ባለፉት 24 አመታት ተግባራዊ የሆነው የጎሳ ፌደራሊዝም ለግጭት መንስኤ መሆኑን በመረጃ ዘርዝሮ ማቅረቡን የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

ይሁንና ኢብኮ ይህን የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልዕክት ‹‹በተለያዩ ጊዜያት በብሔር ብሔረሰቦች መካከል ተከሰቱ ያሉትን ግጭቶች በመዘርዘር በህዝቦች መካከል ሌላ ግጭት እንዲቀሰቀስና እንዲባባስ የሚያደርጉና ግጭት የሚያራግቡ፣ አንዱን ብሔር ከሌላ ብሔር የሚያገጩ ናቸው፡፡›› በሚል እንደማያስተላልፍ ገልጾአል፡፡ ከዚህም ባሻገር በመልዕክቶቹ ውስጥ ‹የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት›፣ እንዲሁም ‹የህወሓት/ኢህአዴግ ስርዓት› የሚለው አገላለጽ የፓርቲውን ህጋዊ መጠሪያ የማይወክል በመሆኑ›› በሚል እንደማያስተላልፍ ገልጾአል፡፡

በሌላ በኩል እነዚህ ግጭቶች በአሁኑ ወቅትም የቀጠሉና የጎሳ ፌደራሊዝሙ እስካለ ድረስ ብዙ ዋጋ የሚያስከፍሉ መሆናቸውን የገለጸው የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ መልዕክቶቹ ከፓርቲው ማንፌስቶ የወጡ፣ ኢብኮ እንዳለው ለግጭት ሳይሆን ከግጭቶቹ መማር እንዲቻልና አሁን ያለው የጎሳ ፌደራሊዝም ከተስተካከለ ችግሮቹ እልባት እንደሚያገኙ በሚያሳይ መልኩ የተላለፈ መልዕክት ነው ብሎአል፡፡ ‹‹እኛ ያቀረብነው አማራጫችን ነው፡፡ አማራጫችን ስናቀርብ ደግሞ የጎሳ ፌደራሊዝም የፈጠረውም ቀውስም በማሳያነት ማቅረብ አለብን፡፡ ይህን እውነታ የአገር ውስጥና የውጭ ተቋማት ዘግበውታል፡፡ አብዛኛዎቹ መንግስትም ያመነባቸው ናቸው፡፡ ነገር ግን ስርዓቱ የሰራቸው ጥፋቶች ይፋ አውጥተን እንዳናቀርብ ስለተፈለገ መልዕክቱን መልሰውታል፡፡ በግልጽ አማራጫችን እንዳናቀርብ ተከልክለናል›› ሲል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

በተመሳሳይ የአዲስ አበባ አስተዳደር መገናኛ ኤጀንሲ የሰማያዊ ፓርቲን የቅስቀሳ መልዕክት ‹‹ከሀገሪቱ ሰንደቅ አላማ ጋር የሚጻረር፣ ብሔር ብሄረሰቦችን ወደ አላስፈላጊ ግጭት እንዲያመሩ የሚገፋፋ፣ የሌላ ፖለቲካ ፓርቲን ስም የሚያጎድፍ ይዘት የተካተተባቸው›› ናቸው በሚል መልሷል፡፡ ይህ የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ሲመለስ ለ8ኛ ጊዜ መሆኑ ነው፡፡

10854971_685322414926753_8423503827339637126_o 10854971_685322414926753_8423503827339637126_o

ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia

The post የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልዕክት ለ8ኛ ጊዜ ተመለሰ appeared first on Zehabesha Amharic.


ድምፃችን ይሰማ 2ኛውን የሰላማዊ ተቃውሞ ይፋ አደረገ * “ሳንቲም በመሰብሰብ በራስ ላይ እቀባን በማድረግ ለመንግስት ተቃውሞን መግለጽ”

$
0
0

SaveYourCoins # EthioMuslimsPeacefulStruggle #Boycott #CivilDisobedience

2ኛው አነስተኛ የትብብር መንፈግ ተቃውሞ መርሃ ግብር
ሳንቲም በመሰብሰብና በማጠራቀም ራስ ላይ የመቆጠብ እቀባ በማድረግ ለመንግስት የተቃውሞ መልእክት ማስተላለፍ
ረቡዕ መጋቢት 16/2007

በሰላማዊ ህዝባዊ ትግል ውስጥ ትብብር የመንፈግ እና የቦይኮት ተቃውሞ ከመንግስት ኃይሎች ጋር ሳይፋጠጡ እና አካላዊ ግጭት ውስጥ ሳይገቡ ትብብርን በመንፈግና የቦይኮት እንቅስቃሴዎችን በማድረግ በደል እያደረሰ ለሚገኘው አካል የተቃውሞ መልእክት የማተላለፍ ስልት ነው፡፡ የትብብር መንፈግ ተቃውሞዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ዓይነቶች ያሏቸው ሲሆን በአገሪቱ ውስጥ የሚገባንን የዜግነት መብት እስክናገኝ ድረስ ለመታገል ቆርጠን በገባንበት ታላቅ ህዝባዊ ትግል ውስጥ ካሁን ቀደም እምብዛም ሳይሞከር ቆይቷል፡፡
yisema
ይሁንና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተቃውሟችን ወደቦይኮት እና ትብብር የመንፈግ ስልቶች እንደሚሸጋገር፣ ይህም አደባባይ ተኮር በሆኑ ተቃውሞዎች የገዛ ህዝቡ ላይ ጥይት ለመተኮስ የማያመነታው መንግስት ጡጫ እንዳያሳርፍብን ለመከላከል እንደሚያስችል መገለጹ ይታወሳል፡፡ እስካሁንም በጥቂት አጋጣሚዎች በቀኑ ክፍለ ጊዜ ስልክን በማጥፋት እና በአስገዳጅ ሁኔታዎች ውስጥ ካልሆነ ባለመጠቀም ውስንና አነስተኛ የቦይኮት ተቃውሞን በኢትዮ ቴሌኮም ተቋም ላይ ለማድረግ ተሞክሯል፡፡ አሁን ደግሞ ትንሽ ከፍ ያሉ የትብብር መንፈግ ስልቶችን ቀስ በቀስ ወደመላመዱ እና ወደመተግበሩ፣ ቀስ በቀስም ወደማሳደጉ መግባት ተገቢ ሆኖ በመገኘቱ ባለፈው ጁሙዓ እየገባንበት ያለውን የትግል ስልት ስኬታማ እንዲያደርግልን እና መሪዎቻችንንም ከእስር ነጃ እንዲልልን በአገሪቱ በሚገኙ መስጂዶች ተሰባስበን ዱዓ ማድረጋችን ይታወሳል፡፡ በመሆኑም ከፊታችን ጁሙዓ መጋቢት 18/2007 ጀምሮ ሳንቲም በመሰብሰብና በማጠራቀም ራስ ላይ የመቆጠብ እቀባ በማድረግ ለመንግስት የተቃውሞ መልእክት ወደማስተላለፍ እንቅስቃሴ የምንገባ ይሆናል፡፡

መንግስት በገዛ ህዝቦቹ ላይ በሃይማኖታችን ምክንያት እያደረሰብን የሚገኘው ከፍተኛ በደል የሚሳለጠው ከእኛው በሚሰበሰብ ግብር መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ህዝቡን እየደበደቡ እና እየገደሉ ያሉት የመንግስት ኃይሎች ደሞዛቸው የሚከፈለውም ከህዝቡ ኪስ በሚወጣ ገንዘብ ነው፡፡ በመሆኑም እንደዜጋ ገንዘባችንን በራሳችን ላይ ኢንቨስት ያለማድረግ የዜግነት መብታችንን በመጠቀም የሳንቲም ዝውውሩ ላይ እጥረት ስንፈጥር በእርግጥም ከእኛ ኪስ የሚገኘው ገንዘብ ላይ እኛም እንደህዝብ የተወሰነ ስልጣን እንዳለን ለመንግስት ግልጽ እናደርጋለን። ጥያቄዎቻችንን ባለመመለሱም የተቃውሞ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡

እንደሚታወቀው መንግስት አንዲትን ሳንቲም ከዓለምአቀፍ የገንዘብ አምራች ተቋማት ሲያሰራ ከዋጋዋ በላይ አውጥቶባት ነው፡፡ ለሳንቲም ማሰሪያ ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠይቅ በመሆኑም ሳንቲም ዝውውሩ ላይ ችግር ሲፈጠር ከፍተኛ ጫና ይደርስበታል፡፡ ምናልባት መንግስት ክፍተቱን ተጨማሪ ሳንቲም በማተም ለመሙላት ቢሞክር እንኳን የሰበሰብነውን ሳንቲም መልሰን ወደ ገበያው በማስገባት የዋጋ ዝቅጠት መፍጠር የምንችልበት አጋጣሚ የሚኖር መሆኑም ከግንዛቤ የሚገባ ነው፡፡ በዚህ የተቃውሞ ዘዴ ልናሳካው የምንሻው ጊዜያዊ ዓላማ ለሶስት ዓመታት ‹‹የፍትህ ያለህ!›› ስንል ቆይተን ከተጨማሪ በደል ውጭ መልስ ላልሰጠን መንግስት እንደህዝብነታችን አቅም እንዳለን እና ተጽእኖ ማሳደርም እንደምንችል ማሳየት ነው – ያለህዝብ ይሁንታ የመንግስት ህልውና ቢዘግኑት የማይዘገን ጉም መሆኑን ማስመስከር!!

ሳንቲም ሰብስቦ የመቆጠቡ ተቃውሞ አተገባበር

1/ የምንሰበስበው እና ቆጥበን የምናስቀምጠው እጃችን ላይ የገባውን ሳንቲም በሙሉ አይደለም! ይልቁንም ለኑሯችን አስገዳጅ የሆነውን ያክል ብቻ በመጠቀም ቀሪውን ማስቀመጥን ዓላማ ያደረገ ነው፡፡ በመሆኑም እጃችን ላይ ከሚገቡት ሳንቲሞች የግድ አስፈላጊ የሆነውን ያክል ብቻ በመጠቀም ቀሪውን በማስቀመጥ ብቻ እንወሰናለን፡፡

2/ ሳንቲም ቆጥቦ የመሰብሰብ ተቃውሞው የሚካሄደው በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች እና ከተሞች ነው፡፡

3/ ሳንቲም ቆጥቦ የመሰብሰብ ተቃውሞው የሚጀምረው የፊታችን አርብ መጋቢት 18/2007 ጀምሮ ሲሆን በዚሁ ገጻችን ማብቃቱ እስኪገለጽ ድረስም ላልተወሰነ ጊዜ ይቀጥላል፤ በአላህ ፈቃድ!

አዎን! እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በሃይማኖታችን ምክንያት በመንግስት ከፍተኛ በደል እየደረሰብን ያለን ሰላማዊ ዜጎች ብንሆንም መንግስት ከበደሉ ሊቆጠብ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ለዓመታት ሰላማዊ ትግል ስናደርግ ቆይተናል፡፡ ሰላማዊነታችንን ለመግለጽ ነጭ ጨርቅ እያውለበለብን በአደባባይ በተገኘን ቁጥር መንግስት አስፈራርቶናል፤ ዘልፎናል፤ ደብድቦናል፤ ዘርፎናል፤ አስሮናል፤ ገድሎናል፡፡ እኛ ነጭ ሶፍት ይዘን ሰላማዊነታችንን በአደባባይ ስንዘምር መንግስት ደግሞ ዝናሩን ታጥቆ በጥይት እሩምታ ተቀብሎናል፡፡ የማይጠፋ ጠባሳ የጣለ ጥቁር ሽብር ፈጽሞብናል፤ ፈርመን የላክናቸውን ወኪሎቻችንን በግፍ እስር እና በከፍተኛ ቶርቸር አሰቃይቶብናል፡፡ እስካሁንም ነጻነታቸውን ነፍጎ የምርጫ ቅስቀሳ መጠቀሚያ እያደረጋቸው ነው። እንግዲህ አሁን ላይ መንግስት ጥይት ሊተኩስበት በማይችለው ሜዳ ሰላማዊ ተቃውሟችንን ከመቀጠል ውጭ ሌላ ምርጫ ያለን አይመስልም፡፡ ዛሬ ይፋ ያደረግነው የትብብር መንፈግ ተቃውሞ ዋነኛ ዓላማም መንግስት ጥይት የሚተኩስበት ዒላማ የማያገኝበትን የትግል ድባብ በመፍጠር መብታችንን የማጎናጸፍ ግዴታውን እንዲወጣ የተቃውሞ መልእክት ማስተላለፍ ነው፡፡ ወደፊትም አንድ ብርና ከዛም በላይ ያሉ የብር ኖቶችንም ከመሰብሰብ ጀምሮ ሌሎች በአተገባበራቸውም ሆነ በእንድምታቸው ጠንክረው እያደጉ የሚሄዱ የትብብር መንፈግ እና የቦይኮት ስልቶችን ቀስ በቀስ በመለማመድ ሰላማዊ ትግላችንን እስከድል ደጃፎች እንቀጥላለን፡፡ ከአላህ ፈቃድ ጋር ይሳካልናል፤ ድልም ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለምና!

ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!
ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

The post ድምፃችን ይሰማ 2ኛውን የሰላማዊ ተቃውሞ ይፋ አደረገ * “ሳንቲም በመሰብሰብ በራስ ላይ እቀባን በማድረግ ለመንግስት ተቃውሞን መግለጽ” appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: ፍቅረኛዬ ቤተሰቦቼ አግቢ ስላሉኝ አግባኝ ወይም እንለያይ የሚል ምርጫ ሰጠችኝ፤ ምን ይሻለኛል?

$
0
0

ፍቅረኛዬ ቤተሰቦቼ አግቢ ስላሉኝ አግባኝ ወይም እንለያይ የሚል ምርጫ ሰጠችኝ፤ ምን ይሻለኛል?
ቢ ነኝ

ውድ ጠያቂያችን ቢ የሁኔታህን አሳሳቢነት ግምት ውስጥ በማስገባት ከሌሎች ደብዳቤዎች ያንተን በማስቀደም ይኸው ፈጣን ምላሻችንን ሰጠንህ፡፡ ከጽሑፍህ እንደተረዳነው በማግባትና በመለየት መካከል አንዱን ለመምረጥ ተቸግረሃል፡፡ ለዚህ ደግሞ መፍትሄው ውሳኔ የመስጠት ክህሎትን (Decision Making Skill) ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ ክህሎት ስር ያሉ የተለያዩ ስልቶችን/techniques/ በማንሳት ላንተ ሁኔታ አቅጣጫ በሚጠቁም መልኩ እናሳይሃለን፡፡
Decisions of Love to make our Marriage Life Successful
እንደዚህ አይነት ውሳኔ ለመስጠት የሚያስቸግሩ ነገሮች በሚያጋጥሙ ጊዜ መጨነቁና መወጣጠሩ የግድ ነው፡፡ ነገር ግን ቁምነገሩ መጨናነቁ ሳይሆን፣ ጊዜ ወስዶ ስለጉዳዩ በጥሞና በማሰብ የመፍትሄ እርምጃ መውሰዱ ነው፡፡ ይህንንም ለማድረግ የመጀመሪያው ተግባር ችግሩን በሚገባ መለየት (Identify the problem) ነው፡፡ ፍቅረኛህ ለምንስ ሁለት አማራጮችን ብቻ ሰጠችህ? በጽሁፍህ እንደገለፅከው ቤተሰቦቿ እንድታገባ ስለፈለጉ ፍቅረኛህን ወጥረው ያዟት እሷም ላንተ ይህንን ምርጫ ሰጠችህ፡፡ ስለሆነም አሁን ያንተ ዋነኛ ችግር እሷን ከማግባትና ከእርሷ ጋር ተለያይቶ በመኖር መካከል መወጠርህ ነው፡፡ ያ ማለት የመጀመሪያው ተግባርህ ችግሩን መለየት ሲሆን ይህንንም ከውነሃል፡፡

ቀጣዩ ተግባርህ፣ ያሉህን አማራጮች በሙሉ ማየት (brain strom all possible option) ነው፡፡ በዚህም መሰረት ያሉህ አማራጮች አንደኛ ቤተሰቧ በሚሰጧችሁ ገንዘብ መሰረግና ከፍቅረኛህ ጋር አብሮ መኖር፣ ሁለተኛ ፍቅረኛህን አለማግባትና ከእሷ ተለይቶ መኖር ሲሆን ሶስተኛ አማራጭም አለህ፡፡ ይህም ፍቅረኛህን በማሳመን የተወሰነ ጊዜ ቆይቶ ራስን አጠንክሮ መጋባት ነው፡፡

ዋናው ጉዳይ ደግሞ ያለው፣ ከእነዚህ አማራጮች ውስጥ አንዱን መምረጡ ላይ ነው፡፡ ይህንንም ለማድረግ ቀጣዩን ተግባር መወሰኑ ወሳኝ ነው፡፡ ይህም እያንዳንዱ አማራጭ በአጭር ጊዜና በረጅም ጊዜ የሚያስከትለውን ጥሩና መጥፎ ነገሮችን መለየት ነው፡፡ ውድ ቢ ሶስቱንም አማራጮች በወረቀት አስፍራቸውና በእያንዳንዱ ስር ያን አማራጭ ብትመርጥ ምን ጥሩ፣ ምንስ መጥፎ ነገሮችን ሊያስከትል ይችላል ብለህ በሚገባ በማሰብ በዝርዝር ጻፋቸው፡፡

ምሳሌ ልስጥህ፤ የመጀመሪያው አማራጭ ፍቅረኛህን ማግባት ነው፡፡ ይህንን አማራጭ ብትተገብረው ተከትሎ ከሚመጡ ጥሩ ነገሮች አንዱ፣ የምትወዳት ፍቅረኛህ ጋር አብሮ መኖር ትችላለህ፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ተከትለው ከሚመጡ መጥፎ ነገሮች ውስጥ አንዱ በሌሎች ገንዘብ ሠርግህን ታከናውናለህ፡፡ እንዲህ እያደረክ ይህንን አማራጭ ብትመርጥ የሚከተሉትን ጥሩና መጥፎ ነገሮችን በዝርዝር ፃፋቸው፡፡ ለሌሎች አማራጮችም በተመሳሳይ ምርጫውን ተከትለው የሚመጡ ጥሩና መጥፎ ነገሮችን ዘርዝረህ ፃፍ፡፡

እዚህ ላይ ሁለት ነገሮችን መናገር ይኖርብኛል፡፡ አንደኛው ይህ ጥሩ ወይም መጥፎ ነገር ይከሰታል ብለህ ብታሰፍር በቂ መረጃዎች መኖራቸውን ማረጋገጥ ይገባሃል፡፡ በሌላ ቋንቋ ለእያንዳንዱ ይከሰታል የምትለው ጉዳይ አላማና የሆነና ምክንያታዊ መረጃ ሊኖርህ ይገባል፡፡ ለምሳሌ ሶስተኛውን አማራጭ ብትመርጥ ፍቅረኛዬን ማሳመን አልችልም የሚል ነገር ብታስቀምጥ፣ ይህ እምነትህ ትክክል ለመሆኑ በቂ የሆነ ማስረጃ ሊኖርህ ይገባል፡፡
ሌላው ጉዳይ ደግሞ ዲካታስትፎፊንግ /Decatastrophing/ የሚባል ስልት አለና ይከሰታሉ የምትላቸውን መጥፎ ነገሮን ስታስቀምጥ ይህን ስልት ተጠቀምበት፡፡ ይህ ስልት ማለት ደግሞ አንድ መጥፎ ነገር ይከሰታል ስትል፣ ነገሩ የመከሰት ዕድሉ ምን ያህል ነው የሚለውን ማጤን፣ የችግሩ መጠን ምን ያህል ክብደት /Magnitude/ ይኖረዋል የሚለውን መገመት ብሎም ችግሩን ከመከሰቱ በፊት ለመከላከል የምትችልባቸውን መንገዶችን ወይም ችግሩ ሊከሰት መቋቋም የምትችልበትን መንገዶች ቀደም ብሎ ማሰብ ማለት ነው፡፡ በምሳሌዎች ላስረዳህ፡፡ አንደኛውን አማራጭ ብትመርጥ ከሚከተሉት መጥፎ ነገሮች አንዱ ራሳችሁን ሳትችሉ ልጅ መውለድ ይመጣል የሚል ነገር አሰፈርክ እንበል፡፡ በዚህ ጊዜም ልጅ የመውለድ እድላችሁ ምን ያህል ነው፡፡ ልጅ ቢወለድ የሚከሰትባችሁ ችግር ምን ያህል ነው እና ልጅ እንዳትወልዱ ማድረግ የምትችሉባቸው መንገዶች ወይም ልጅ ቢወለድና ችግር ውስጥ ብትገቡ እንዴት አድርጋችሁ ችግሩን መቋቋም እንደምትችሉ ማሰብ ማለት ነው፡፡ በተቃራኒው አማራጭ ሁለትን ብትመርጥ ከፍቅረኛህ ጋር መለያየት ተከትሎ የሚመጣ መጥፎ ነገር ነው ብለህ አሰብክ እንበል፡፡ ስልቱንም በተግባር ለማዋል አንጋባም ብትላት፣ ፍቅረኛህ ጥላህ የመሄድ ዕድሏን ማጤን፣ ጥላህ ብትሄድ ምን ያህል እንደምትጎዳ መገመትና ጥላህ እንዳትሄድ ማድረግ የምትችልበትን መንገዶች ወይም ጥላህ ስትሄድ የሚደርስብህን ጉዳት ለመቋቋም የምትችልበትን መንገዶች ማሰብ ይኖርብሃል፡፡
በአጠቃላይም፣ እያንዳንዱ አማራጭ ብትመርጠው ተከትለው የሚመጡ ጥሩና መጥፎ ነገሮን በዝርዝር ማብሰልሰልና በጽሑፍ ማስቀመጥ ዋናው ጉዳይ ነው፡፡ በመቀጠል ደግሞ ከሶስቱ አማራጮች ብዙ ጥሩ ነገሮችን የሚያስከትለውን ወይም ብዙ መጥፎ ነገሮች የማያስከትለውን አንዱን አማራጭ መምረጥ፣ ብሎም በዛ ምርጫህ ምክንያት ሊመጡ የሚችሉ ጉዳቶችን አምኖ ለመቀበል ራስን ማዘጋጀት ነው፡፡

እዚህ ላይ አንድ ነገር ልጠቁምህ፡፡ አሁን አንተ እየመረጥክ ያለኸው ምርጫ እንደ ሌሎች አይነት ምርጫዎች /ለምሳሌ ሁለት ቦታ ስራ አልፈህ አንዱን መምረጥ/ ቀላል አይደለም፡፡ ለዚህ ደግሞ አይነተኛ ምክንያቱ አንተ እየመረጥካቸው ያሉ አማራጮች ስሜታዊ የሆኑ ጉዳዮች (emotional component) አሉት፡፡ የብዙ ዘመን ፍቅረኛን ማጣት የሐዘን ስሜት፣ እሷን ከቤተሰቦቿ በሚገኝ ገንዘብ ማግባት የተረጅነት ስሜት፣ እሷን አሳምኖ ሰርጉን ማዘግየት በእሷ በኩል የመናደድ ስሜት፣ ባንተ በኩል እሷን ለማሳመን የትዕግስት መፈተን ስሜት፣ ወዘተ በውሳኔህ ውስጥ አብሮ ይኖራል፡፡ እንደነዚህ አይነት ስሜታዊ ጉዳዮችን ለመወሰን የስነ ልቦና ባለሙያዎች ጥሩ ስልት የሚሉት፣ ከእያንዳንዱ ምርጫ ጋር የሚመጡ ሁኔታዎችን ማጤን ብሎም ራስን ውሳኔው በሚነካው ሰው ቦታ የማስቀመጥ ስልትን (reattribution) መጠቀም ወሳኝ ነው፡፡ በመሆኑም ፍቅረኛህን አላገባሽም የሚለውን ውሳኔ ለማሳወቅ ከመነሳትህ በፊት፣ ራስህን በፍቅረኛህ ቦታ አድርገህ፣ ላገባ ነው የሚለውን ውሳኔ ለቤተሰቦችህ ከማሳወቅህ በፊት፣ ራስህን በቤተሰቦች ቦታ አድርገህ፣ የተወሰነ ጊዜ ጠብቂኝ ብለህ ለፍቅረኛህ ከመናገርህ በፊት እራስህን በፍቅረኛህ ቦታ አስቀምጠህ ወዘተ ማሰቡ ጠቃሚ ነው፡፡

አንዱን አማራጭ ከመረጥክና በምርጫህ የተነሳ የሚመጣውን ነገር ለመቀበል ከተዘጋጀህ በኋላ፣ የመጨረሻ ተግባርህ የወሰንከውን ለፍቅረኛህ ማሳወቅ ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ደግሞ ሁለት ዘዴዎችን መጠቀሙ ጠቃሚ እንደሆነ ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ አንደኛው ፍቅረኛህ ራሷን በአንተ ቦታ እንድታስቀምጥና ውሳኔ እንድትሰጥ መጠየቅ (Reattribution) ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ካንተ ሁኔታ ጋር ተመሳሳይ የሆኑ ታሪኮችን በመንገር (story telling) ወደ ራስህ ውሳኔ የማሳወቅ ተግባር መሄድ ነው፡፡ ብሌን ኪኖር የተባለ ምሁር በ2005 እ.ኤ.አ በሰራው ጥናት ለሰዎች የሌሎችን ታሪክ መናገር፣ ሰዎቹ ሀሳባቸውን እንዲቀይሩ ወይም ቢያንስ የእኛን ሁኔታ እንዲረዱና እንደሚያደርጋቸው አሳይቷል፡፡ ስለሆነም አንተ ተመሳሳይ ታሪኮችን በመንገርና ፍቅረኛህ ባንተ ቦታ ሆና እንድትወስን በማድረግና ውሳኔህን በማሳወቅ በውሳኔህ መሰረት በመንቀሳቀስ ውጥረትህን ማርገብ ትችላለህ፡፡ በስተመጨረሻም እላይ የጠቀስኳቸውን ተግባራት በቅደም ተከተል በመተግበር፣ ከችግርህ እንድትወጣ እያሳሰብኩ መልካሙን በመመኘት የዛሬ ምላሼን በዚሁ አጠናቀቅሁ፡፡

The post Health: ፍቅረኛዬ ቤተሰቦቼ አግቢ ስላሉኝ አግባኝ ወይም እንለያይ የሚል ምርጫ ሰጠችኝ፤ ምን ይሻለኛል? appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ‹‹እግርኳስ ህይወቴ ነው›› –ዲያጎ ኮስታ

$
0
0

diago costa
የፎቶ ስቱዲዮው የሚገኝበት ስፍራ ከቴምስ ወንዝ ብዙም አይርቅም፡፡ ሱሬይ በመባል በሚታወቀው የከተማዋ ክፍል አንድ ጥግ ላይ ይገኛል፡፡ ዲዬጎ ኮስታ በስራ ተጠምዶ የሚታየው በዚያ ነው፡፡ ዳግም ለቅጣት ላለመዳረግም ጥንቃቄ ያደርጋል፡፡ ጊዜውን በሚገባ ለመጠቀም በእነዚህ ቀናት ከስፖንሰሮቹ ጋር የሚሰራውን ስራ እያስኬደ ነው፡፡ ያለፉት ጥቂት ሳምንታት ለእርሱ አስደሳች አልነበሩም፡፡ ባለፈው ወር መጨረሻ ማንቸስተር ሲቲ ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ መጥቶ ሰማያዊዎቹን ሲገጥም በጉዳት ከሜዳ ከራቀው ሴስክ ፋብሪጋዝ ጋር በመሆን በደጋፊዎች መካከል ተቀምጠው ጨዋታውን ተከታተሉ፡፡ በቪላ ፓርክ ቡድናቸው ያደረገውን ጨዋታ ከነጭራሹ በስታዲየም ተገኝተው አልተከታተሉም፡፡ ቼልሲ ኤቨርተንን በጠባብ ውጤት ያሸነፈበትን ጨዋታ ግን ታድመዋል፡፡ ‹‹መጫወት አለመቻል ያበሳጫል፡፡ ሜዳ ላይ ተገኝቼ የቡድን ጓደኞቼን መርዳት አለመቻሌ ያናድደኛል፡፡ ባለፉት ጨዋታዎች ላይ እንደተመለከትነው ጨዋታው ፈታኝ ከሆነ አደብ ገዝቼ መመልከት አይሆንልኝም፡፡ ኳስ በተመታ ቁጥር እቁነጠነጣለሁ፡፡ ተረጋግቼ የምመቀጠው የጨዋታው ውጤት አስተማማኝ ከሆነ አልያም ቡድኔ የበላይነት ከወሰደ ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን በቀላሉ ስሜታዊ እሆናለሁ››

ያንን ከ15 ቀናት በፊት ከአጥቂው ፊት ለፊት የተቀመጡ ተቀያሪ ተጨዋቾች ሊመሰክሩ ይችላሉ፡፡ በተመልካች እና ተቀያሪዎች መካከል የነበረውን መለያ አጥር በተደጋጋሚ በቡጢ ሲነርት ተመልክተዋል፡፡ ገለልተኞች ይህ ሁሉ ነገር እንዲሆን ያደረገው ኮስታ እራሱ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ በካፒታል ዋን ካፕ ሊቨር ፑልን ሲገጥሙ ኤምር ቻንን ባይረግጥ ኖሮ ለቅጣት ባልተዳረገ ነበር ይላሉ፡፡ አሰልጣኙ በተደጋጋሚ ውሳኔውን ተቃውመው ተናግረዋል፡፡ ጉዳዩ ሲነሳባቸው እንደ አዲስ ንድድ ይላሉ፡፡ አጥቂው በጉዳዩ ዙሪያ ብዙ እንደተናገረ ያስባል፡፡ ከአሁን በኋላ በተመሳሳይ ርዕስ ላይ ላለመነጋገርም ወስኗል፡፡ ነገር ግን ጥፋተኛ አይደለሁም በሚለው አቋሙ እንደፀና ነው፡፡

ግጭት አስደሳች አልነበረም፡፡ ነገር ግን ተንኮል አይታይበትም፡፡ ‹‹ሆን ብዬ አላደረግኩትም፡፡ ቪዲዮውን መመልከት ይቻላል›› ያንን ስለሚያምን ፀፀት በውስጡ የለም፡፡ አቋሙም ግልፅ ነው፡፡ አጨዋወቱን የሚቀይርበት ምንም አይነት ምክንያት የለም፡፡ በውድድር ዘመኑ መጀመሪያ አካባቢ በማንቸስተር ሲቲዎቹን ቨንሶ ካምፓኒ እና ፓብሎ ዛባሌታ እንዲሁም በሊቨርፑሎቹ ማርቲን ስክርትል እና ማማዶ ሳኮ ላይ የበላይነት እንደወሰደው ሁሉ በሌሎቹም ላይም ማድረጉ አይቀርም፡፡ ባለፈው የውድድር ዘመን የአትሌቲኮ ተጨዋች ሳለ በቻምፒዮንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ ቼልሲን ሲረቱ ጆን ቴሪን ማስጨነቁም አይዘነጋም፡፡

ሁልጊዜ የተወዳዳሪነት መንፈስ በውስጤ አለ፡፡ ያንን ያምናል፡፡ ‹‹ወደ ሜዳ ስገባ እለወጣለሁ›› በማለት ማረጋገጫ ይሰጣል፡፡ ያ ባይሆን ኖሮ በ19 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 17 ጊዜ ኳስ እና መረብ ማገናኘት ባልቻ ነበር፡፡ ኤምር ቻን ላይ የፈፀመው ጥፋት ብዙ ነገሮችን ያስታውሳል፡፡ ዳኞች እና የእግርኳስ ተንታኞች አጋጣሚውን ጨከን ባለ እይታ ሊገልፁት ይችሉ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አንድ የማይካድ ሐቅ አለ፡፡ የተጋጣሚ ቡድን ተጨዋቾች ትንሿን ንክኪ አጋንነው የማቅረብ ባህል አላቸው፡፡ ያንን የሚያደርጉት የተጋጣሚን ተጨዋች ለመተንኮስ ነው፡፡ ‹‹ለረዥም ጊዜ የከላካዮች ኢላማ ሆኜ ቆይቻለሁ፡፡ በእነርሱ መጎሸምን ተለማምጄዋለሁ፡፡ ሲጥሉኝም በቶሎ እነሳለሁ›› ሲል ተሞክሮውን ያካፍላል፡፡

‹‹ያንን አውቃለሁ፡፡ አንዳንድ ተከላካዮች ለትንሽ ንክኪ ተቃውሞ ሲያቀርቡ ብሰማም መታገሌን እና ሸርተቴ መውረዴን አላቆምኩም፡፡ ለእኔ ሁሉም ነገር የሚጠናቀቀው ጨዋታው እንደተፈፀመ ነው፡፡ ሁሉንም ነገር ሜዳ ውስጥ ትተን እጅ ለእጅ ተጨባብጠን እንወጣለን፡፡ አልቢትሩ የተበሳጨሁት እና አላስፈላጊ ድርጊት የፈፀምኩት ስንት ጊዜ ከተረገጥኩ እና ከተመታሁ በኋላ እንደሆነ ከግምት ሊያስገባ እንደሚገባ አስባለሁ፡፡ በእንግሊዝ የሚገኙ አልቢትሮች ብቃት ያላቸው ናቸው፡፡ በሜዳ ውስጥ ሊከሰት የሚችለውን ነገር ይገነዘባሉ፡፡ ያንን ከግምት ያስገባሉ፡፡
‹‹ወደ ሜዳ የምገባው የተለየ አላማ ይዤ አይደለም፡፡ ድክመቱን እጠቀማለሁ ብዬ አንድ የተወሰነ ተጨዋችን መርጬ ወደ ሜዳ አልገባም፡፡ ከጨዋታ በፊት ያንን ካደረግክ ከዋነኛ አላማህ ትስተጓጎልና ወደ አላስፈላጊ ግጭት ታመራለህ፡፡ በዚህ ምክንያት በጥሩ ሁኔታ መጫወት ይሳንሃል፡፡ ሜዳ ውስጥ ልንነታሪክ እንችል ይሆናል፡፡ ንክኪዎችም ይኖራሉ፡፡ ነገር ግን የታቀደበት ነገር አይደለም፡፡ ስሜት ነው፡፡ ፍልሚያ ነው፡፡ የተለየ ዕቅድ የሚባለውን ነገር እርሱት፡፡ ብቸኛ አላማዬ ጎል ማስቆጠር እና ለቡድኔ ጠቃሚ በሆነ መንገድ መጫወት ነው፡፡ ከእኔ የሚጠበቀው በጥሩ አቋም ላይ ለመገኘት መሞከር እና ያንን ማሳካት ነው›› በማለት የቀድሞው የአትሌቲኮ አጥቂ ስሜቱን ያካፍላል፡፡
Diego Costa

ባለፈው የውድድር ዘመን በላሊጋው ከየትኛውም ተጨዋች በላይ ፋውል ተሰርቶበታል፡፡ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ሊዮኔል ሜሲ እንኳን የእርሱን ያህልጥፋት አልተፈፀመባቸውም፡፡ ጥፋት ሲሰራበት ላለመውደቅ የሚያደርገው ከፍተኛ ጥረት የቡድን ጓደኞቹ ያደንቁለታል፡፡ ያንን ሲመለከቱ ይበረታሉ፡፡ እርግጠኝነትም ይሰማቸዋል፡፡ በቪሴንቴ ካልዴሮንም ሆነ በቤርናቢዮ ሰርጂዮ ራሞስ የፈፀመበትን ተደጋጋሚ አስቀያሚ ጥፋቶች ታግሶ አልፏል፡፡ ነገር ግን ብራዚላዊው የስፔን ዜግነት እንዲቀበልያግባባው ይኸው ተከላካይ ነው፡፡ በውድድር ዘመኑ የመጀመሪያ ጨዋታ በርንሌን ለመግጠም ከማምራታችሁ በፊት ከቴሪ ጋር ተገናኝቶ የአጨዋወት ዘይቤው እንዲደግፍለት አግባብቶታል የሚል ወሬ ሲናፈስ ነበር፡፡ ተቀባይነት ያገኘም ይመስላል፡፡ ያንን በሚያደርግበት ወቅት ይህንን የመሰለ ቅጣት ሊያጋጥመው እንደሚችል ግን ሊገነዘብ ይገባል፡፡ ነገር ግን የ26 ዓመቱ ተጨዋች ትልቅ ሃብት መሆኑን የቡድን ጓደኞቼ ያውቃሉ፡፡

ተጋፊነቱ እንግዳ ነገር አይደለም፡፡ በእግር ኳስ እዚህ ለመድረስ ያለፈበት አስቸጋሪ ጉዞ ነፀብራቅ ነው፡፡ በላጋርቶ ጎዳናዎች ላይ ልቡ የደነደነ ተጨዋች ባህሪይ ነው፡፡ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ተጋሪዎቹ በሀብታም ክለቦች ስር በሚገኙ አካዳሚዎች አላደገም፡፡ ቤተሰቦቹን ትቶ በ2 ሺ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደምትገኘው ሳኦፖሎ ያመራው ገና በ14 ዓመቱ ነው፡፡ በዚያ ኤድሰን በተባለ አጎቱ ሱቅ ስራ መስራት ጀመረ፡፡ ባርሴሎና ኢስፓርቲቮ ካፔላ በሚባል በከተማዋ ደቡባዊ ክፍል በሚገኝ ክለብ አቅሙን ማሳየት ጀመረ፡፡ 100 ፓውንድ ወርሃዊ ደመወዝ ይከፈለው ጀመር፡፡
ኮስታ የመጀመሪያውን ‹‹ፕሮፌሽናል›› ጨዋታ ያደረገው በባርሴሎና ኡሲ ነው፡፡በዚያ በወጣት ቡድኑ ጥሩ አቋም አላየ፡፡ ወደ ፖርቱጉኤዛ፣ ሳኦ ፓውሎ እና ፓልማይራስ ይዘዋወራል የሚሉ ጭምጭምታዎች ተናፈሱ፡፡ ነገር ግን እውን አልሆኑም፡፡ በ18 ዓመት ለዝነኛው ወኪል ሆርጌ ማንዴዝ የሚሰራ ወኪል ተመለከተው፡፡ ከዚያም በአውሮፓ ከክለብ ክለብ መዟዟር ጀመረ፡፡ ሜንዴዝ ተጨዋቹን በመጀመሪያ ያስቆጠረው በብራጋ ነው፡፡ በስፔን እና ፖርቹጋል በሚገኙ አምስት ክለቦች በውሰት ተጫውቷል፡፡ በእነዚህ ዓመት አራት ቋሚ ዝውውሮች አድርጓል፡፡ ያ ወቅት አለመረጋጋት የሞላበት ነበር፡፡ እራሱን እስከ መጠራጠር ደርሷል፡፡ ነገር ግን ያደገው ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ አትሌቲኮ እርሱን ሁለት ጊዜ እንዲያስፈርመው አድርጓል፡፡ በ2007 ከብራጋ አስፈረመው፡፡ ከሶስት ዓመት በኋላ ደግሞ ከቫያዶሊና፡፡ ተጫዋቹ ስኬታማ ለመሆን ያለው ተነሳሽነት ወደር የለውም፡፡
‹‹እግር ኳስ ህይወቴ ነው፡፡ እራሴን በሌላ ሥራ ውስጥ ላስብ አልችልም፡፡ የማስበው ሜዳ ውስጥ ገብቼ ስለመጫወት ብቻ ነው›› ሲል ዲያጎ ኮስታ ማብራራቱን ይጀምራል፡፡ ‹‹እዚህ ለመድረስ ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፌያለሁ፡፡ በዚህ ደረጃ እራስህን ከምርጥ ተጨዋቾች ተርታ አሰልፈህ ለመቀጠል የተሻለ ተጨዋች እና የተሻለ ግለሰብ መሆን ይጠበቅብናል፡፡ በመሆኑም ምንም ነገር ለነገ ሳልተው ጠንክሬ መስራት ይጠበቅብኛል፡፡ ባለኝ ነገር ደስተኛ ነኝ፡፡ ሰዎች ይመኩብሃል፡፡ እዚህ ለመድረስ የተጓዝኩበት መንገድ በተለየ እይታ ልመለከተው ይገባል፡፡ የተመኘሁላቸውን አይነት ህይወት ለቤተሰቦቼ በመስጠቴ ደስተኛ ነኝ፡፡ የእኔ ኃላፊነት ያ ነው፡፡››

እርስዎ ከዚህም በላይ አድርጓል፡፡ በሰሜን ምስራቅ ብራዚል በምትገኘው እና ወደ 100 ሺ የሚጠጉ ነዋሪዎች ባሏት የትውልድ ከተማው ላጋርቶ የሚገኘውን ቦላ ዴ ኡሮ የተባለ ለትርፍ ያልተቋቋመ የእግርኳስ ‹‹አካዳሚ›› በገንዘቡ ይደግፋል፡፡ አካዳሚው ከወዲሁ የአካባቢውን ኩራት ሆኗል፡፡ እርሱ ታዳጊ በነበረበት ወቅት በዚያ የነበረው ሰፋፊ ጎዳናዎች አቋርጠውት የሚያልፉት ሜዳ ነበር ትልልቅ የእርሻ መኪኖች ሲመጡ የልምምድ መርሃ ግብሮችን ለተወሰነ ጊዜ ማቋረጥ የግድ ነበር፡፡

አሁን ለውጦች እየታዩ ነው፡፡ አካዳሚው በመሻሻል ላይ ነው፡፡ በአቅራቢያው ወደሚገኝ የትምባሆ እርሻ አጠገብ ተዘዋውሯል፡፡ አስፈላጊ የሆኑ መሳሪያዎች ተሟልተውለታል፡፡ አደረጃጀቱ እና መዋቅሩም ተስተካክሏል፡፡ የህክምና ማዕከል፣ የመማሪያ ክፍሎች እና ሶስት የቤት ውጪ የመጫወቺያ ሜዳዎች አሉት፡፡ በእነዚህ ላይ የማስፋፊያ ስራ ለመስራትም ተዘጋጅተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በአካዳሚው ዕድሜያቸው እስከ 17 ዓመት የሚደርስ 230 የአካባቢው ተወላጆች ይገኛሉ፡፡ አካዳሚው ከወዲሁ በአካባቢው በጎ ተፅዕኖ እያሳረፈ ነው፡፡

ባለፈው ክረምት በተከናወነው የዓለም ዋንጫ የስፔንን ማልያ ለብሶ ወደ ሜዳ ሲገባ አብዛኞቹ ብራዚላውያን ተበሳጭተውበታል፡፡ ንዴታቸውን በዘለፋ እና ስድብ ገልፀዋል፡፡ በላጋርቶ ዋነኛ አደባባይ ግን ስሜቱ የተለየ ነበር፡፡ በዕለቱ ስፔን ሆላንድን ስትገጥም አብዛኞቹ ቀዩን የስፔን ማሊያ ለብሰው ነበር፡፡ በዚህም ደስተኛ ነው፡፡

‹‹ወደ ኋላ መለስ ብዬ አሰብኩ፡፡ ህልሜን እውን ለማድረግ ላጋርቶን ለቅቆ ስሄድ በዚያ የነበረውን ነገር አውቃለሁ፡፡ ፕሮጀክቱን የጀመርኩት በወኪሌ ድጋፍ ነው፡፡ እርሱ ከዓለም ምርጥ ተጨዋቾች የተወሰኑት ደንበኛ ነው፡፡ በመሆኑም በዚያ የሚገኙ ልጆች መንገዱ እንዲመቻችላቸው ተስፋ አደረግኩ፡፡ በዚያ ያሉ ልጆች እኔ ያላገኘሁት ዕድል ይመቻችላቸዋል፡፡ በቤተሰቦቸው አቅራቢያ ይኖራሉ፡፡ ከጎዳና ህይወት እና ከአደንዛዥ ዕፅ ይርቃሉ፡፡ በጥሩ ከባቢ ውስጥ ያድጋሉ፡፡ የተሻለ አቅጣጫ የሚያመላክታቸው ያገኛሉ፡፡

‹‹ላጋርቶ ትንሽ ከተማ ናት፡፡ እግር ኳስ ተጫዋች መሆን የሚፈልጉ ህፃናት በቂ ምቹ አጋጣሚ አያገኙም፡፡ በመሆኑም ይህ ፕሮጀክት ዕድል ይሰጣቸዋል፡፡ በማዕከሉ የሚሰሩ ትልልቅ ፕሮፌሽናሎች አሉን፡፡ ወሳኙ ነገር ያ ነው፡፡ መዋቅሮቹ ገና በመሻሻል ላይ ናቸው፡፡ ነገር ግን እዚህ በነበርኩበት ወቅት ከነበሩት የተሻሉ ሜዳዎች በአካዳሚው ይገኛሉ፡፡ ምግብ፣ ጥሩ ህክምና እና ድጋፍም ይሰጣቸዋል፡፡ የጎደለ ነገር የለም፡፡ ልጆች በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በሚሆኑበት ወቅት መምህራን እና አሰልጣኞች በሙሉ ተነሳሽነት ይረዷቸዋል፡፡ የአካዳሚው ዋነኛ አላማ ፕሮፌሽናል እግርኳስ ተጨዋቾችን ማፍራት ሳይሆን ታዳጊዎቹን በዕውቀት ማነፅ ነው፡፡ የቀለም ትምህርትን መከታተል ግዴታ ነው፡፡በትምህርቱ ደካማ የሆነ ልጅ በልምምድ መረሃ ግብሮ ተሳታፊ እንዲሆን አይፈቀድለትም፡፡ አንዳንዶቹ ልጆች እግርኳስ ተጫዋች አይሆኑ ይሆናል፡፡ ነገር ግን በአካዳሚው ውስጥ በማለፋቸው የተሻሉ ሰዎች ይሆናሉ፡፡ ከሚያጡት ይልቅ የሚያገኙት ይበልጣል›› በማለት ዲያጎ የፕሮጀክቱን አላማ እና ግብ ይገልፃል፡፡
የራሱን ትሩፋት ትቶ ለማለፍ መፈለጉ ክፋት የለውም የሚያስመሰግነው ነው፡፡ ይህ ድርጊቱ ኮታን በተለየ መንገድ ይገልፀዋል፡፡ ሰዎች እንደሚያስቡት ከፊቱ የቆሙትን ሁሉ ረጋግጦ የሚያልፍ አለመሆኑንም ያሳያል፡፡ የአትሌቲኮ ተጨዋች በነበረበት ወቅት ከሄታፌ ጋር ሲጫወቱ ኳስ እና መረብ ለማገናኘት ሲጥር ለከፍተኛ ጉዳት ተጋልጧል፡፡ በእርግጥ እንዳሰበው ኳስ መረብ ላይ አረፈች፡፡ እርሱ ግን ከቋሚው ጋር ተላትም ተሰበረ፡፡ በወቅቱ አሰልጣኝ ዲያጎ ሲሞን ያዘነው ለቋሚው ነበር፡፡ ‹‹ጭረት ነብርን አይጎዳም፡፡ የማዝነው ለቋሚው ነው›› ብሏል የአትሌቲኮው አሰልጣኝ፡፡

ኮስታ አጋጣሚውን ሲያገኝ በአግባቡ ተጠቀመበት፡፡ ሰርጂዮ አጉዌሮ፣ ራዳሜል ፋልካኦ እና ዲያጎ ፎርላን ለቅቀው ሲሄዱ ክፍተቱን እርሱ ደፈነ፡፡ በሁለት የውድድር ዘመናት 56 ጎሎን አስቆጠረ፡፡ ቼልሲ 32 ሚሊዮን ፓውንድ የከፈለው ብቃቱን ላረጋገጠ ተጨዋች ነው፡፡
‹‹በአትሌቲኮ በነበርኩበት ወቅት በለውጥ ሂደት ውስጥ ነበርኩ፡፡ በየዓመቱ ለመሻሻል ጥረት አደርጋለሁ፡፡ የሚቀርፅህ ሰው ማግኘት ወሳኝ ነው›› ይላል ኮስታ፡፡ ‹‹ጆዜ ሞውሪንሆ ከእኔ ምን እንደሚፈልግ ያውቃል፡፡ ጎል ከማስቆጥር በተጨማሪ ታትሬ እንድሰራ ይፈልጋል፡፡ ለታታሪነት ቅድሚያ ይሰጣል የእስካሁኑ የቼልሲ ቆይታዬ መልካም ነው፡፡

‹‹በስኳዱ ውስጥ የአንድነት መንፈስ አለ፡፡ ባለፈው የውድድር ዘመን በአትሌቲኮ ከነበረው መንፈስ ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ሁላችንም የምንፈልገው ተመሳሳይ ነገር ነው፡፡ የስራ ባህላችንም የምንፈልገው ተመሳሳይ ነገር ነው፡፡ የስራ ባህላችንም አንድ አይነት ነው፡፡ እንደ ቡድን ውጤታማ ለመሆን ያንን ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ሴስክ ፋብሪጋዝን የመሰለ ተጨዋች በቡድን ውስጥ ማግኘቴ አግዞኛል፡፡ በስፔን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የጎል አጋጣሚዎችን የሚፈጥርልኝ መሆኑ ጠቅሞኛል፡፡ ኳስ የማቀበል ብቃቱ ያስገርማል፡፡

ሁለቱ ተጨዋቾች ከወዲሁ ደመነፍሳዊ ግንኙነት መስርተዋል፡፡ ኮስታ የእንግሊዝን እግርኳስ የለመደበት ፍጥነት ደግሞ ያስገርማል፡፡ ኮስታ ወደ ሜዳ የሚመለሰው ከየትኛውም ጊዜ በላይ ልዩነት ለመፍጠር ተነሳስቶ ነው፡፡ ምንም እንኳን ፊቱ ላይ የፌዝ ፈገግታ የነበረ ቢሆንም ከቼልሲ የአሰልጣኞች ስታፍ አባላት አንዱ ‹‹ቅዱስ›› ብሎ ጠርቶታል፡፡ እርሱስ እራሱን የሚገልፀው እንዴት ነው? ‹‹አዎን ይስማማኛል፡፡ ቅዱስ ብላችሁ ጥሩኝ›› ሲል በፈገግታ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

The post Sport: ‹‹እግርኳስ ህይወቴ ነው›› – ዲያጎ ኮስታ appeared first on Zehabesha Amharic.

ያልመከተ ተፈነከተ፤ ያልተደራጀ ተፈጀ። –ጌታቸው ኃይሌ

$
0
0
getachew

ጌታቸው ኃይሌ

አንዱን የዘመናችንን ትልቁን ብሔራዊ ችግር ለመፍታት ያስችል የመሰለኝን ሐሳብ ከጥቂት ቀናት በፊት “በኢትዮጵያ ሰላም የሚያመጣ የአማራ የተራድኦና የዕርቅ ድርጅት ያስፈልጋል” በሚል ርእስ አንድ ጽሑፍ በ ethiomedia ለሕዝብ አቅርቤ ነበር። በጽሑፉ ጥቂት ሰዎች የተወያዩበትን ወዳጆች ልከውልኝ አነበብኩት። በስልክ ያወያዩኝም አሉ። ትችቶቹን ሁሉ ስላላየኋቸው ይሆናል እንጂ፥ ያየኋቸውን ሳጠናቸው፥ ከዶክተር ፀሐይ ብርሃነ መስቀል በቀር ፍሬ ነገሩ ላይ ያተኮረ ሐሳብ የሰጠ አላጋጠመኝም።

የተቺዎችን ቀልብ የማረከው “አማራ የሚባል ሕዝብ አለ ወይስ የለም?” የሚለው ነው። ይኸንን መተቸት ደስ ይላል መሰለኝ፥ ተተችቶ ባለቀ በስንት ዓመቱ፥ ትችቱ እንዲያገረሽበት ጽሑፌ ምክንያት ሆነ። እኔ ግን ጽሑፌን የደመደምኩት እንዲህ ብየ ነበር፤

ለዚህ ድርሰት አስፈላጊነቱ ስላልታየኝ፥ “አማራ ማነው?” ከሚል፥ መልሱ ብዙ ገጽ ከሚፈጅ ጥያቄ ውስጥ አልገባሁም። ሁሉም ራሱን ስለሚያውቅ፥ “አማራ ነኝ” የሚል ሁሉ በሙሉ አባልነት፥ በድርጅቱ የዕርቅና የሰላም ዓላማ የሚያምን፥ ግን “አማራ ነኝ” የማይል ኢትዮጵያዊ ደግሞ በደጋፊ አባልነት መመዝገብ ይችላል።

እንዲህ ያልኩት መተቸቱ ተስኖኝ አይደለም። እንዲያውም ካሁን በፊት ማስረጃ እየሰጠሁ በሰፊው እንደተቸሁት የሚያስታውስ አይጠፋም። አሁን እንደገና ያልተቸሁት፥ ታኝኮ የተዋጠን በማመስኳት፥ የኔንም የአንባቢውንም ጊዜ ላለማጥፋት መርጬ ነበር። “አማራ አለ” የሚሉም “አማራ የለም” የሚሉም፥ እንደየመነሻቸው ተቀባይነት ያለው ምክንያት አላቸው። በዘር ከሄድን የዘመን ብዛት ስላዳቀለን፥ ዛሬ አማራ የሚባል ዘር አለ ለማለት አይቻልም፤ የለም። በባህል ከሄድን ግን አለ። አማራ ከማለት አማርኛ ተናጋሪ ማለት የሚመረጠውም ስለዚህ ነው። ይህ የባህል ሕዝብ ለመኖሩ ማስረጃው ቀላል ነው፤

አንደኛ፥ “አማራ ነን” የሚሉ ሰዎች አሉ። “አማራ አይደላችሁም” ብንላቸው ግራ ይጋቡና፥ “ታዲያ ምን ልታደርጉን ነው፤ ዶርዜ፥ ወይስ እስላም?” ብለው ሊጠይቁ ይችላሉ።

ሁለተኛ፥ ብዙ ሰዎች “አማራ ናችሁ” ተብለው ተገድለዋል፥ ከሀገራቸው ተፈናቅለዋል፥ ንብረታቸው ተዘርፏል። “አማራ አይደላችሁም” የተባሉ ጎረቤቶቻቸው፥ ወይም በአውቶቡስ ላይ አብረዋቸው የተቀመጡ ተሳፋሪዎች ግን አማሮች አይዶሉም ተብለው ድነዋል።

ሦስተኛ፥ በየዘመኑ የሚደረገው የሕዝብ ቈጠራ ሕዝቡን በጎሳ ሲመድብ አማራውን የለህም ብሎ አልዘለለውም። የአማራው ቍጥር መቀነሱን ያወቅነው፥ በቈጠራው አማካይነት ነው። ቈጣሪዎቹ በዚህ መንገድ መሄዳቸው ተሳስተዋል እንዳንል፥ በማንም አገር የሚደረግ ነው። አሜሪካ ረዘም ያለ ጊዜ እየኖረ፥ ይኸንን ልምድ ያልደረሰበት ያለ አይመስለኝም።

አራተኛ፥ አንድ ቋንቋ ለሌለ ነገር ስም አያወጣም፤ “አማራ” የሚል ቃል ወይም መጠሪያ ስም በቋንቋችን ውስጥ ካለ፥ በዚያ ስም ተጠሪ ሕዝብ አለ ማለት ነው።

አምስተኛ፥ “ኢትዮጵያውያንን በዘር መከፋፈል ይሆናል” ተብሎ ቀረ እንጂ፥ የቀድሞ መታወቂያ ደብተር ላይ “ዘር” የሚል መሥመር ነበረበት፤ ያለምክንያት አልነበረም። ምንጮቹ “ቤተ አምሐራ” ይሏቸዋል።

ግን አንድ እውነታ አለ። አማራው (ወይም አማርኛ ተናጋሪው) ራሱን እንዳንድ የተለየ ሕዝብ ቈጥሮ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ራሱን አላገለለም። ማለት፥ አንድነቱ በኢትዮጵያዊነቱ ነው እንጂ በአማራነቱ ላይ አይደለም። በሀገር ጉዳይ ላይ ጎሳ ሳይለይ ከሁሉም ጋር አብሮ ይሠራል። እንዲቀጥልበት ማበረታታት የሁላችን ግዴታ ነው። ግን ጥቃትን ለመከላከል መጠራራትና ዘዴ መፍጠር እንኳን በሰዎች በእንስሳት ዘንድም ያለ ነገር ነው። እንድ ኢትዮጵያዊ፥ “አማራ ነህ” እየተባለ ሲጨፈጨፍና ማንም ሰው ሳይደርስለት ዝም ብሎ ይታይ ወይ? ሌላው ቢቀር “ነግ በኔ” አይደለም ወይ? የሚል ጥያቄ ተነሥቷል። ጥያቄው ተገቢ ነው ወይስ አይደለም? አማርኛ ተናጋሪው እንዳይደርስለት ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ተለይቶ የአማራ ወገን መፍጠር ሆነበት። ምን ይሻላል?

ለዚህ መልስ ሳሰላስል ችግሩ በተለይ የአማራው ሕዝብ ሳይሆን የሀገሪቷ ሆኖ ታየኝ። አገሪቷ አማርኛ ተናጋሪውን በጎሳዎች የሚያስጠላ ጠላት (ጸላኤ ሠናያት የሚባለው ሰይጣን) ገብቶባታል። ስለዚህ የጥላቻውን ምንጭና ምንጩን መድፈኛ ዘዴ ወደመፈለግ ሄድኩት። ምንጩ ወያኔ ብዙዎቹን ጎሳዎች በአማራው ላይ በጠላትነት ማስነሣቱ፥ መፍትሔው ደግሞ፥ “በኢትዮጵያ ሰላም የሚያመጣ የአማራ የተራድኦና የዕርቅ ድርጅት” መሆኑን ለሕዝብ አቀረብኩ። ከአንባቢዎቼ የጠበቅሁት፥ ሐሳቡ የማያዋጣ ከመሰላቸው፥ ምክንያት ሰጥቶ ውድቅ ማድረግ፤ የሚያዋጣ ከሆነ፥ ተከታትለነው ከዚህ ትልቅ ብሔራዊ በሽታ እንፈወስ የሚል ነበር። ሰው ግን የጽሑፌን ቁም ነገር ወደጎን ትቶ፥ የሚያውቀውን ለመናገርና ብሶቱን ለመተንፈሻ አጋጣሚ አደረገብኝ። (1) አማራ አለ፤ (2) አማራ የለም፤ (3) አማራ በዘር መዘጋጀት የለበትም ለማለት ብዕር መዘዛ መጣ። ግን ሦስቱም የጽሑፌ የኅዳግ ነጥቦች እንጂ አስኳሎች አይደሉም።

ዶክተር ፀሐይ ብርሃነ መስቀል ብቻ የዕርቅ ድርጅ የማቋቋሙን ሐሳብ ደግፋ፥ ድርጅቱ በአካባቢ (regional) ቢሆን ይሻላል የሚል አማራጭ አቅርባለች። ግን ሐሳቧ የችግሩን መንሥኤ ይስታል። የተከሰሰው በአንድ አካባቢ ያለ ሕዝብ ሳይሆን፥ አማራው ተለይቶ ነው።

ሌላ ወዳጄ፥ በድርጅቱ ውስጥ አማራ ያልሆኑ ቢገቡበትስ የሚል ሐሳብ አቀረበልኝ። ይኸም የችግሩን መንሥኤ ይስታል። የተከሰሰው አማራው ተለይቶ ነው። ሌሎች እንደ አማራው ተከስሰው እንደ አማራው አልተጨፈጨፉም። ጽሑፌ ያተኮረው ወያኔ በሚያጠቃው ላይ ሳይሆን፥ ወያኔ በሚያስጠቃው ላይ ነው።

ፕሮፌሰር ሀብተ ጊዮርጊስ በዘር መደራጀትን (ከሞተበት) አናስነሣው የሚል ተማፅኖ አቀረበ። ጽሑፌን ባይጠቅስም የተማፀነው የኔ ሐሳብ ተቀባይነት እንዳያገኝ መሆኑ ግልጽ ነው። ይህን ጽሑፍ ያረቀቅሁት የሱን ጽሑፍ ስላየሁ ነው። የምናካሂደው ውይይት ሀገር የሚጠቅም መፍትሔ ለማግኘት ስለሆነ፥ ስሜትን ገታ አድርገን ከተወያየን፥ ልንግባባ እንዲያውም ከአንዳች ስምምነት ላይ ልንደርስ እንችላለን።

የፕሮፌሰር ሀብተ ጊዮርጊስ ተማፅኖ እንደገባኝ፥ በጎሳ ከመደራጀት በዲሞክራሲ ላይ የተመሠረቱ ሥራዎች እንሥራ የሚል ነው። የዕርቅ ድርጅት ማቋቋምና በዲሞክራሲ ላይ የተመሠረቱ ሥራዎችን መሥራት ሲስማሙ እንጂ ሲጋጩ አይታየኝም። ልብ አላልነውም ይሆናል እንጂ፥ በባህል መደራጀት ከሰው ልጅ ጋር አብሮ የተፈጠረ ነው። ለምሳሌ፥ ክርስቲያኖች በሃይማኖት ተደራጅተው ከፓርትያርክ (ከፖፕ) እስከ ዲያቆን የራሳቸው አስተዳዳሪዎችና አገልጋዮች አሏቸው። ከዚያም አልፎ፥ የዓለም-አቀፍ አብያተ ክርስቲያን ማኅበር አለ። ሙስሊሞችም ተመሳሳይ ድርጅት አላቸው። የአንድ ሰፈር ሰዎች እድር አላቸው። የነጋዴዎች ምክር ቤት አለ። በዓለም ላይ በሚደርስ ድንገተኛ አደጋ ለሚጎዱ ችግረኞች ፈጥነው የሚደርሱላቸው እንደ ቀይ መስቀል ያሉ የክርስቲያኖች የተራድኦ ድርጅቶች ናቸው። ዕርቅና ሰላም ለማምጣት አማሮችን ማደራጀት የሚኮነን ከሆነ፥ መጀመሪያ እነዚህ ድርጅቶች መኮነን፥ ቤተ ጸሎቶችም መዘጋት አለባቸው።

ዲሞክራሲ ያወጀልን ትልቁ ፍልስፍና ሰዎች ዘርንና ሃይማኖትን መሠረት ያደረገ የፖለቲካ ፓርቲ እንዳያቋቁሙ በሕግ መከልከልን ነው። ጽሑፌን የደመደምኩትም፥ በአንድ ሀገር ውስጥ የሚቋቋም የፖለቲካ ፓርቲ መሠረት የሚያደርገው ሁሉን እኩል አብሮ በሚያሳድግ የኢኮኖሚ ፍልስፍና ላይ ነው፤ ሕዝብን በዘርና በባህል የሚከፋፍል ድርጅት ግን “በሕግ መከልከል፥ መኰነንም አለበት። ለመረዳዳት፥ ከዚያም አልፎ ሌሎችን ለመርዳት ከሆነ ግን፥ በሕግ መፈቀድ፥ መደገፍም አለበት” በማለት ነው። እባብ ያየ ልጥ ቢያይ በራየ፤ የጎሳ ድርጅትን ጉዳት ያየ የተራድኦና የዕርቅ ድርጅትን ቢያይ በራየ ሆኖ ነው እንጂ፥ ድርጅቱ ስሕተት ኖሮበት አይደለም። ያልመከተ ተፈነከተ፤ ያልተደራጀ ተፈጀ የምለው ኢትዮጵያን ነው።

 

The post ያልመከተ ተፈነከተ፤ ያልተደራጀ ተፈጀ። – ጌታቸው ኃይሌ appeared first on Zehabesha Amharic.

ቴዲ አፍሮ ገንዘብ ለሚወዱና ለገንዘብ ለሚሞቱ አዲስ ግጥም ጻፈ

$
0
0

teddy afro
*** ለፍቅር በቀር*** (የቴዲ አፍሮ አዲስ ግጥም)

አትቁጠሩ ገንዘብ ንዋይ አትደርድሩ
በፍቅር በቀር ከንጉሱ ስለማታድሩ
ያላቹት አይገባውም ቋንቋው ይለያል
ፍቅር ብቻ ዘምሩለት ያኔ ይሰማቹሃል
መግባቢያው ነውና ፍቅር ያደገበት
ለህሊናው ሊኖር ኪሱን የጠላበት
ፍቅር ብቻ በሉት ካለበት ይመጣል
ከነፍስ ከስጋው ፍቅር ተዋህዷል
ግድ አይሰጠውም ገንዘብ ቢደረደር
ልቡ አይደነግጥም ለፍቅር በቀር
ሃብቴ ብሎ ይዟታል ቀሪ ንብረቴም
በፍቅር በቀር መንገስ አይፈልግም
አባት ነው አባትነት አይቼበታለው
ቸር ነው ያለውን ሲሰጥ አይቻለው
ፍቅር ነው ፍቅርን ሲዘምር ሰምቻለው
ይህ ብላቴና በመዋደድ ነው የሚያምነው
ከነፍስ ከስጋው ፍቅር ተዋህዷል
ፍቅር ብቻ በሉት ካለበት ይመጣልX2

The post ቴዲ አፍሮ ገንዘብ ለሚወዱና ለገንዘብ ለሚሞቱ አዲስ ግጥም ጻፈ appeared first on Zehabesha Amharic.

የኢትዮጵያ አየር መንገድን እንሻረክህ የሚሉ አየር መንገዶች መበርከታቸው ተዘገበ…

$
0
0

Ethiopian Airlineየኢትዮጵያ አየር መንገድ በአራት የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ የእቃ አጓጓዥ አየር መንገዶችን ለማቋቋም እቅድ እንዳለው ብሉምበርግ የወሬ ምንጭ ዘገበ፡፡ አየር መንገዱ ከዚህ ቀደምም እንደ ማላዊ እንዲሁም የቶጎው አስካይ አየር መንገዶች ውስጥ ድርሻ እንደገዛና የባለቤትነት እጅ እንዳለው የሚዘነጋ አይደለም፡፡
አሁን ላይ ከናይጄሪያ መንግስት በኩል ለግዙፍ ባለኢኮኖሚ አፍሪካዊቷ ሀገር የእቃ ጫኝ አየር መንገድ በማቋቋም በኩል እንዲሳተፍ ጥሪ እንደቀረበለት የተነገረው አየር መንገዱ በሌሎች ሶስት የአፍሪካ ሀገራት ውስጥም ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ለመጀመር በሚያስችል መንገድ ላይ ንግግሮች መጀመራቸውን የወሬ ምንጩ የአየር መንገዱን ዋና ስራ አስኪያጅ ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
ብሉምበርግ ዋና ስራ አስኪያጁን አቶ ተወልደ ገብረማሪያምን ጠቅሶ እንደዘገበው ከሆነ በሌሎች አየር መንገዶች ውስጥ ገብቶ የመሳተፍ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች አየር መንገዱ እንደቀረቡለትና ይህንን በሚመለከትም ተቋሙ የቢዝነስ ጥናቶችን በማካሄድ ላይ እንዳለ ተናግሯል፡፡
የኢትዮጵ አየር መንገድ በሰውም ሆነ በእቃ መጫን መጓጓዣ አገልግሎቶቹ ከአፍሪካ እጅግ ጠንካራ አየር መንገድ እንደሆነ ያስነበበው ዘገባው ለነዚህ በሽርክና የእንስራ ጥያቄዎች መቅረብም ዋነኛ ምክንያት ይሄው መሆኑን ነው የሚተነትነው

The post የኢትዮጵያ አየር መንገድን እንሻረክህ የሚሉ አየር መንገዶች መበርከታቸው ተዘገበ… appeared first on Zehabesha Amharic.

በኦሮሚያ እና ሌሎች አካባቢዎች የመጠጥ ውሃ ችግር ት/ቤቶችን ከማዘጋት አልፎ ለስደት እየዳረገ ነው

$
0
0

ኢሳት ዜና :- 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በመቶ ሚሊየን በሚገመት ወጪ በታላቅ ፌሽታ እያከበረ የሚገኘው የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) አመራር በአንዳንድ የኦሮሚያ አካባቢዎች ትምህርት ቤቶችን እስከማዘጋት የደረሰውን የመጠጥ ውሃ ችግር ሊታደግ ያልቻለ መሆኑን መረጃዎች ጠቆሙ፡፡

ከግብርና ሚኒስቴር የወጣ አዲስ መረጃ እንደሚያሳየው፣ በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የተከሰተው የመጠጥ ውሃ ችግር ሕዝብን ለከፍተኛ ችግር ከመዳረጉም አልፎ የመማር ማስተማር ስራ በማደናቀፍ ትምህርት ቤቶችን እስከማዘጋት ደርሷል።
water line
የመጠጥ ውሃ ችግር ከገጠማቸው የኦሮሚያ አካባቢዎች መካከል በአርሲ ዞን በጎሎልቻ፣ መርቲ፣ .ዝዋይ፣ ዱግዳ፣ ሴሩና ደጁ ወረዳዎች፣ በምዕራብ አርሲ ዞን በሻላ ሲራሮና ሻሸመኔ ወረዳዎች፣ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን በሚደጋ፣ ቁምቢያ መዩ ወረዳዎች፣ በምስራቅ
ሸዋ ዞን በቦሰት ወረዳ እና በጉጂ ዞን በሊበንና ሰባቦሩ ወረዳዎች አስከፊ የተባለ የመጠጥ ውሃ ችግር ማጋጠሙን ሚኒስቴሩ አጋልጦአል፡፡
የመጠጥ ውሃ ችግሩ በተለይ በአርሲ ዞን በዝዋይ ዱግዳና በሴሩ ወረዳዎች፣ በጉጂ ዞን በሊበን ወረዳ ት/ቤቶችን እስከማዘጋት የደረሰ ችግር መከሰቱ ተረጋግጦአል፡፡ በእነዚህ አካባቢዎች የተከሰተውን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ ሚኒስቴሩ ከአጋር ድርጅቶች
ባገኘው ድጋፍ ውሃ በቦቴ የማደል ስራ እያከናወነ መሆኑ ታውቋል፡፡

በቦረና ዞን አንዳንድ ወረዳዎች ማለትም በአሬሮ፣ ድሬ፣ ዲሎ፣ ዳስ የእንስሳት መዳከምና ሞት መከሰት የጀመረ ሲሆን በአርሲና ምዕ/ሐረርጌ ዞኖች የእንስሳቱ አቋም እየተዳከመ መሆኑ፣ የእንስሳት እንቅስቃሴም ተጀምሮ በምዕ/ሐረርጌ ዞን ከቡርቃ ዲምቱና ሃዊ
ጉዲና ወደ ዱንገታና ዋቤ ወንዝ፣ በቦረና ዞን ከተልተሌ ወደ ገራንና ኮንሶ፤ ከድሬ፤ ሚዮና ሞያሌ ወደ ኬንያ (አዋሳኝ ቦታዎች) በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸው በሪፖርቱ ተመልክቷል።

የኦሮሚያ ክልል ገዥ ፓርቲ ኦህዴድ/ኢህአዴግ እንዲህ ዓይነቱን የህዝብ ችግር ሳይፈታ ለክብረበአል በመቶ ሚሊየን ብሮችን ሲያፈስ መታየቱ አሳዛኝ መሆኑን ዘጋቢያችን ያነጋገርናቸው የኦሮሞ ተወላጆች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በአማራ ክልል ደግሞ በሰ/ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ፣ በሰ/ጎንደር ዞን በምስራቅ በለሳ ወረዳ በእያንዳንዳቸው 3 ቀበሌዎች የውሃ እጥረት፣ በዋግኸምራ ዞን በሳህላ፣ ዝቋላና ሰቆጣ ወረዳዎች፣ በሰ/ወሎ ዞን በላስታና ቡግና ወረዳዎች፣ በደ/ወሎ ዞን በመቅደላ
ወረዳ በ4 ቀበሌዎች፣ በኦሮሚያ ዞን በአ/ፉርሲ ወረዳና በምስ/ጎጃም ዞን ቆላማ አካባቢዎች የውሃ እጥረት ተከስቷል።
በሀረሪ ክልል በ5 ቀበሌዎችና በድሬዳዋ አስተዳደር ቆላማ ቀበሌዎችም ተመሳሳይ ችግር ተከስቷል። ችግሮችን ለመቅረፍ ውሃ በቦቴ ለማደል ሙከራ መደረጉም በሪፖርቱ ተጠቅሷል።

The post በኦሮሚያ እና ሌሎች አካባቢዎች የመጠጥ ውሃ ችግር ት/ቤቶችን ከማዘጋት አልፎ ለስደት እየዳረገ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.


ድምጻችን ይሰማ:- ሳንቲም ሰብስቦ የመቆጠቡ ተቃውሞ አተገባበር -

$
0
0

santim
1/ የምንሰበስበው እና ቆጥበን የምናስቀምጠው እጃችን ላይ የገባውን ሳንቲም በሙሉ አይደለም! ይልቁንም ለኑሯችን አስገዳጅ የሆነውን ያክል ብቻ በመጠቀም ቀሪውን ማስቀመጥን ዓላማ ያደረገ ነው፡፡ በመሆኑም እጃችን ላይ ከሚገቡት ሳንቲሞች የግድ አስፈላጊ የሆነውን ያክል ብቻ በመጠቀም ቀሪውን በማስቀመጥ ብቻ እንወሰናለን፡፡

2/ ሳንቲም ቆጥቦ የመሰብሰብ ተቃውሞው የሚካሄደው በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች እና ከተሞች ነው፡፡
3/ ሳንቲም ቆጥቦ የመሰብሰብ ተቃውሞው የሚጀምረው የፊታችን አርብ መጋቢት 18/2007 ጀምሮ ሲሆን በዚሁ ገጻችን ማብቃቱ እስኪገለጽ ድረስም ላልተወሰነ ጊዜ ይቀጥላል፤ በአላህ ፈቃድ!

አዎን! እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በሃይማኖታችን ምክንያት በመንግስት ከፍተኛ በደል እየደረሰብን ያለን ሰላማዊ ዜጎች ብንሆንም መንግስት ከበደሉ ሊቆጠብ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ለዓመታት ሰላማዊ ትግል ስናደርግ ቆይተናል፡፡ ሰላማዊነታችንን ለመግለጽ ነጭ ጨርቅ እያውለበለብን በአደባባይ በተገኘን ቁጥር መንግስት አስፈራርቶናል፤ ዘልፎናል፤ ደብድቦናል፤ ዘርፎናል፤ አስሮናል፤ ገድሎናል፡፡ እኛ ነጭ ሶፍት ይዘን ሰላማዊነታችንን በአደባባይ ስንዘምር መንግስት ደግሞ ዝናሩን ታጥቆ በጥይት እሩምታ ተቀብሎናል፡፡ የማይጠፋ ጠባሳ የጣለ ጥቁር ሽብር ፈጽሞብናል፤ ፈርመን የላክናቸውን ወኪሎቻችንን በግፍ እስር እና በከፍተኛ ቶርቸር አሰቃይቶብናል፡፡ እስካሁንም ነጻነታቸውን ነፍጎ የምርጫ ቅስቀሳ መጠቀሚያ እያደረጋቸው ነው። እንግዲህ አሁን ላይ መንግስት ጥይት ሊተኩስበት በማይችለው ሜዳ ሰላማዊ ተቃውሟችንን ከመቀጠል ውጭ ሌላ ምርጫ ያለን አይመስልም፡፡ ዛሬ ይፋ ያደረግነው የትብብር መንፈግ ተቃውሞ ዋነኛ ዓላማም መንግስት ጥይት የሚተኩስበት ዒላማ የማያገኝበትን የትግል ድባብ በመፍጠር መብታችንን የማጎናጸፍ ግዴታውን እንዲወጣ የተቃውሞ መልእክት ማስተላለፍ ነው፡፡ ወደፊትም አንድ ብርና ከዛም በላይ ያሉ የብር ኖቶችንም ከመሰብሰብ ጀምሮ ሌሎች በአተገባበራቸውም ሆነ በእንድምታቸው ጠንክረው እያደጉ የሚሄዱ የትብብር መንፈግ እና የቦይኮት ስልቶችን ቀስ በቀስ በመለማመድ ሰላማዊ ትግላችንን እስከድል ደጃፎች እንቀጥላለን፡፡ ከአላህ ፈቃድ ጋር ይሳካልናል፤ ድልም ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለምና!

ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!

The post ድምጻችን ይሰማ:- ሳንቲም ሰብስቦ የመቆጠቡ ተቃውሞ አተገባበር - appeared first on Zehabesha Amharic.

ሚካዔል በላይነህ “የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወርቃማ ዘመን” ትንሳዔ ሰንደቅ ነውን?

$
0
0

(ዳኝነት መኮንን እና ማስረሻ ማሞ)

በኢትዮጵያ የሙዚቃ አድናቂዎች ዘንድ ተወዳጅነትን ካተረፉት የልብ አድርሶች አንዱ ድምጻዊ ሚካዔል በላይነህ ነው። “ሕይወትን ከምንጯ ጠጣሁ ተመልሼ” እያለ ሲዘፍን በእርሱ ሙዚቃ ሌሎች ሕይወትን ከምንጯ ደግመው እንዲጠጡ ያደርጋል ቢባልም የተሳሳተ ሚዛን አይመስለንም።
michael belayneh

የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊዎች በሚካዔል ዘፈን ጉዳይ ከበርካታ የሙዚቃ ባለሞያዎች ጋራ ሲወያዩ የሚነሳው አንድ ዋነኛ ነጥብ አቀንቃኙ የ60ዎቹ ወርቃማ የሙዚቃ ዘመን ትንሳዔ ዐይተኛ ትዕምርት (exceptional symbol) መኾኑ ነው። ከዚህ ተነስተን በ7 ኪሎ መጽሔት የመጀመርያ ዕትም ላይ ይህ ርእሰ ጉዳይ ቢዳሰስ ተገቢ ይኾናል ብለን ሁለት ኹነኛ ጭብጦችን አንስተናል።

1ኛ) ሚካዔል የፈረንጅ ዘፈን የግጥም ሐሳቦችን ወደ አማርኛ በመተርጎም ወደ ሙዚቃው ዓለም ጎራ ብሎ፤ ጥልቅ የኾነውን የኢትዮጵያውያንን ኑሮና ሕይወት ወደሚበረብረው ሙዚቃ እንዴት ሊሻገር ቻለ? የሚለው ቀዳሚው ጭብጥ ሲኾን የዚህ ፊቸር ጸሐፊዎች በሚካኤል የሙዚቃ ዕድገት ላይ ሐሳብ የሚሰጡ ደርዘን የሙዚቃ ባለሞያዎች አነጋግረዋል።

2ኛ) የሚካዔል የቅርብ ጊዜ የሙዚቃ ሥራዎች የብዙሃን ብልሃት (collective wisdom) ውጤት ናቸው። አንዳንድ ባለሞያዎች የሙዚቃውን ሙጡቅነትም ከዚህ የመነጨ እንደኾነ ይገምታሉ። ታዲያ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወርቃማ ዘመን የባተው የብዙሃን ብልሃት በግለኛ መክሊቶች (individual talents) ላይ የበላይነት በመቀዳጀቱ ይኾን?” ከ1950ዎቹ መጀመርያ እስከ 1960ዎቹ መጨረሻ ባለው ጊዜ የኪነ ጥበብ ዛር ከጠርሙሱ የወጣበት ዘመን ነበር ብለው ለመናገር የሚደፍሩ ብዙ የሙዚቃ ባለሞያዎች እና የኢትዮጵያ ሙዚቃ አጥኚዎች አሉ። እነዚህ ባለሞያዎች በዚህ “የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወርቃማ ዘመን” እየጎመራ የመጣው የብዙሃን ብልሃት የአንድን ድምጻዊ ሥራ ውብ ለማድረግ ትልቅ አስተዋጽዖ ሳያበረክት አይቀርም ብለው ያትታሉ። ሐሳቡ እንዲህ ነው፤ በዚያ ዘመን ገጣሚው አምጦ የወለደውን፣ ዜመኛው በምናቡ ያረገዘውን፣ ሙዚቀኛው በመሣርያው ምናብን ከግጥም ጋራ እየፈተለ . . . እያባዘተ . . . የሙዚቃ ልቃቂት ሰርቶ፤ ሁሉም በጋራ የሸመኑትን ለአድማጩ የነፍስ ፍሰሐ ያቀብላሉ። እነዚህ ባለሞያዎች ይህን አቋማቸውን ለማስደገፍ በሶሻል ሳይንስ እና ኔትዎርክ ቲዮሪ የሕዝብ ብልሃት (wisdom of crowds) ላይ የተደረጉ ምርምሮችን ማጣቀሻ ያደርጋሉ።

ይኹንና እነዚህ ባለሞያዎች ወርቃማ በሚሉት ዘመን የተነሱ እንደ እነ ምንሊክ ወስናቸው፣ ጌታቸው ካሳ፣ ግርማ በየነ፣ ሰይፉ ዮሐንስ እና ወዘተ . . . የግለኛ መክሊት ባለቤቶች ነበሩ። እነዚህ ምሳሌዎች የብዙሃን ብልሃትን መላ ምት ፉርሽ የሚያደርጉ ናቸውን? በፊቸራችን በጊዜው የነበሩ የበርካታ ታዋቂ አቀንቃኞችን ሥራዎች በመመርመር ብዙሃኑ የትኛውን እንደሚከተሉ ለማየት ሞክረናል። ያገኘነው ውጤት የባለሟያዎቹን ሐሳብ የሚያረጋግጥ ነው።

ከዚያ በሁዋላ የቡድን የፈጠራ ሥራ ውጤት የኾኑት ሙዚቃዎች ብዙ አቀበት እና ቁልቁለት እያስተናገዱ እስከ 1990ዎቹ ዘልቀዋል። በዚህ ላይ-ታች ውስጥ ጥቂት የማይባሉ የግለኛ መክሊት ባለቤቶች ታይተዋል፥ ንዋይ ደበበ ለ1970ዎቹ አጋማሽ እና ለ1980ዎቹ ዐይነተኛ ትዕምርት ተደርጎ ቢወሰድ የተገባ ነው። ከ1980ዎቹ አጋማሽ ጀምሮ አንድ ሰው ራሱ ገጣሚ፣ ራሱ ዜመኛ፣ ራሱ አቀናባሪ መኾን ሥጦታ ብቻ ሳይኾን ፋሽን ኾነ። በዚህ ወቅት ላይ ይሠሩ የነበሩት አብዛኛዎቹ ሥራዎች የፋሽኑ ተከታዮች ኾኑ። ከእነዚህ በግል መክሊተኞች መካከል አንዳንዶቹ በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ላይ አሻራቸውን ጥለው ያለፉ ናቸው።

ከእነዚህ መካከል እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) እና ቴዲ አፍሮ (ቴዎድሮስ ካሳሁን) ይገኙበታል። እጅጋየኹ ሽባባው ነፍሷ የሚወደውን ሥራ ሠራች። አብዛኛዎቹ ዘፈኖቿ በሰው ልጅ ሕይወት ላይ የሚያጠነጥኑ፣ ታሪክን መሠረት ያደረጉ፣ ብሔርተኝነትን የሚያጸኑ እና ሰው መኾንን የሚያስታውሱ ናቸው። የቴዎድሮስ ካሳሁን ሥራዎች ደግሞ ማንነትን የሚያጠይቁ፣ ፍቅርን የሚሰብኩ፣ ፖለቲካን የሚጓጉጡ እና ብሔርተኝነትን የሚያንጹ ናቸው።

የሙዚቃ ባለሞያዎቹ እነዚህ ጥቂት ዘፋኞች የሂደቱ አዎንታዊነት መገለጫዎች ሳይኾኑ ከተራው ጎራ የማይመደቡ (outliers) እንደኾኑ ይናገራሉ። በግለኛ መክሊቶች ዘመን የተፈጠሩ አብዛኞቹ ሙዚቃዎች በጥራት ቀድሞ ከነበረው በጋራ ሲታዩ ያነሱ ናቸው። የሚካዔል ሙዚቃዎች ይህን የግለኛ መክሊት መጋረጃ ሸነቆረ፤ ይሸረክተው ይኾን?

ማሳረጊያ

እውን ሚካዔል በላይነህ “የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወርቃማ ዘመን” ትንሳዔ ትዕምርት ነውን? ሚካዔል ወደ ሙዚቃው ዓለም ሲመጣ “አንተ ጎዳና – አንተ መንገድ”ን ይዞ ተከሰተ። መንገድ እያናገረ መጣ። መንገድን እንደ አንድ ገጸ ባሕርይ ጥያቄ እየጠየቀው አዜመ። ይህ ዐይነቱ አመጣጥ ብዙም የተለመደ አይደለም። የመጀመርያው አልበሙ አብዛኞቹ ዘፈኖች ሐሳባቸው ከእንግሊዝኛ የተወሰዱና ወደ አማርኛ የተተረጎሙ ናቸው። “ይህ ተጽዕኖ ምናልባት በየክለቡ በሚዘፍንበት ጊዜ ድምጹን የፈታው በእንግሊዝኛ ዘፈኖች ስለኾነ ይኾናል” ብለው የሚሄሱ ባለሙያዎች አሉ። “ሙዚቃው እንደ ወንዝ የሚፈስ፣ የተረጋጋና ስክነት የተሞላበት ነው” የሚሉ ማሞካሻዎች የሚቀርቡለት ሚካዔል፥ በወቅቱ አስቀድሞ ለቆት በነበረው ነጠላ ዜማ ራሱን አስተዋውቆ ስለነበር ወደ አድማጮች ለመድረስ ብዙም አልተቸገረም ቢባል ስህተት አይኾንም።
michael

የሚካዔል ሁለተኛ ሥራ “መለያ ቀለሜ” የሚል አልበም ነው። ይህ ሥራው “ሙዚቃ ማለት ቺክቺካ ነው” ወይም “ለክለብ አስረሽ ምቺው ድለቃ የሚኾን ነው” ብለው ከሚያስቡና ከሚያምኑ አድማጮች ጋራ የማይሰናሰል ነው የሚሉት ሃያሲዎች፤ “የሚካዔል “መለያ ቀለሜ” ጸጥታ የረበበበት፣ ተመስጦ የሚያሻው፣ ጊዜ፥ ቦታ፥ እና ተመክሮ ተውበው የተቀመሩበት ምጡቅ ነገር ግን ዩኒቨርሳል ሥራዎች አካትቷል” በማለት “መለያ ቀለሜ”ን ውዳሴ ያዘምኑለታል። በዚህ መወድስ የማይስማማ አንድ ሃያሲም “ለአንዳንድ አድማጮች ነፍስ የሚያሳርፍ የሚባል ዐይነት ነው እንጂ፥ “መለያ ቀለሜ” ዩኒቨርሳል አይደለም” ሲል ሽንጡን ገትሮ ይከራከራል። በ“መለያ ቀለሜ” አልበሙ ሚካዔል “ጥልቅ የኾኑ ሐሳቦችን ያዘሉ፣ ማንነትን የሚበረብሩ፣ ግጥም ብቻ ሳይኾን የተዋጣለት ሰዓሊ የቀመራቸው ሥዕሎችም እንድሚቀባ ተሰድረዋል” የሚሉ ማሞካሻዎችም በበዙ ሃያሲዎች ተችሮታል። የግርማ ይፍራሸዋ ፒያኖ ከሚካዔል ድምጽ ጋራ ተሰናስሎ በጸጥታ ሲደመጥ (እጅግ ተጋነነ ካልተባለ) የደከሙ የደም ስሮችን ያነቃቃል . . . በእያንዳንዱ የሰውነት ክፍል ውስጥ እንደ ወንዝ ይፈሳል። የዚህ ሙዚቃ ምሥጢር ሌላ አይደለም። እውን የሚካዔልን “መለያ ቀለሜ” የብዙሃን ብልሃት ዳግም መወለድ ነው ልንል እንችል ይኾን? ሚካዔል ድምጹን ይዞ መጣ፤ እነ ጌትነት እንየው አምጠው የወለዱትን ምጡቅ ድርሰት ሰጡት፣ ግርማ ይፍራሸዋ ከፒያኖው ውስጥ አዕዋፍን የሚያስንቅ የሙዚቃ ሕብር ፈጠረ።

ከዚያስ? ሚካዔል ወደየት እየተጓዘ ነው? ከ“መለያ ቀለሜ” በኋላ ይዞት የመጣው ሣልሳዊ አልበሙ “ናፍቆት እና ፍቅር” የብዙኃን ብልሐት (collective wisdom) ልቆ ታይቶበት ይኾን? ይህ ቅምሻ ነው፤ ለዚህ እና ለሌሎች ጥያቄዎች መልስ ሙሉውን ጽሑፍ በ7 ኪሎ መጽሔት ላይ ይጠብቁ!

Source: 7 ኪሎ መጽሔት

The post ሚካዔል በላይነህ “የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወርቃማ ዘመን” ትንሳዔ ሰንደቅ ነውን? appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ዋና አሰልጣኙን ያሰናበተው ቅዱስ ጊዮርጊስ በረዳቶቹ እየተመራ የሱዳኑን ሜሪክ ይገጥማል

$
0
0

st george
ኢትዮኪክ ኦፍ እንደዘገበው ዋና አሰልጣኙን ያሰናበተው ቅዱስ ጊዮርጊስ በረዳቶቹ እየተመራ የወዳጅነት ጨዋታን ከሱዳኑ ሜሪክ ጋር ሊያደርግ ነው::
የሱዳኑ አል ሜሪክ ክለብ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ቅ.ጊዮርጊስ የወዳጅነት ጨዋታውን ከአል ሜሪክ ክለብ ጋር የፊታችን ሰኞ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚያካሄድ ይሆናል።የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም ለጨዋታው እውቅና ሰጥቶታል።
በዚህ ጨዋታ ወቅትም የስታዲየም መግቢያ ትኬት ዋጋም ክቡር ትሪቡን 200 ብር፣ ጥላ ፎቅ 100 ብር፣ ከማን አንሼ ባለ ወንበሩ 50 ብር፣ ከማን አንሼ 10፣ ካታንጋ 7፣ ዳፍ ትራክ እና ሚስማር ተራ 5 ብር መሆኑን የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ አስታውቋል፡፡

The post Sport: ዋና አሰልጣኙን ያሰናበተው ቅዱስ ጊዮርጊስ በረዳቶቹ እየተመራ የሱዳኑን ሜሪክ ይገጥማል appeared first on Zehabesha Amharic.

“ጦር ሠራዊቱ ሕዝባዊ እምቢተኛነት ሲያይል የወያኔን መቃብር ይቆፍራል”–አርበኞች ግንቦት 7

$
0
0

የአርበኞች ግንቦት 7 ወቅታዊ መጽሐፍ

ጉዞአችን ወደ ነፃነት ነው!! መዳረሻችንም የነፃነት አደባባይ ብቻ ነው!!

አለማችን አንባገነን ስታስተናግድ ወያኔ የመጀመሪያው አይደለም። ዘረኛንም እንዲሁ …….. እኛም ስለነፃነት ብለን ለትግል ሰንነሳ የመጀመሪያዎቹ አይደለንም …… አለማችን እንደየዘመኑና እንደ የወቅቱ አንባገነኖች ያለ የሌለ የመሳሪያና ወታደራዊ ሀይላቸውን በመጠቀም ህዝብን በፍርሀት አሸማቀውና ረግጠው ለመግዛት ሲውተረተሩ በተደጋጋሚ ታይተዋል። በዚያው ልክ ህዝባዊ ሀይልና መመከት ተስኗቸው ሲንኮታኮቱ በተደጋጋሚ የታየ ወደፊትም አናባገነኖች እስከተከሰቱ ድረስ በህዝባዊ ሀይል ተጠራርገው መቀመቅ ሲወርዱ መታየቱ አይቀሬ ነው ። ህዝብ የወደደውን አስተዳዳሪ እንጂ ረግጦ ሊገዛው የሚፈልገውና አንባገነን ተቀብሎ አያውቅም ፤ዛሬም አልተቀበለም ፤ ነገም አይቀበልም ። ይህን በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ በተደጋጋሚና በጉልህ የሚታይ ግዙፍ እውነት መቼም ተቀብለውና ከታሪክ ተምረው ስለማያውቁ አሳፋሪው ውድቀታቸው በተደጋጋሚ ሲታይ አለ።
ginbot 7
ሀገራችን የአለማችን አካል እንደመሆኗ አንባገነኖች ተፈራርቀውባታል። አንባገነኖችም በህዝባዊ ሀይል ተጠራርገውባ ታል። ከደቡብ አፍሪካ ቀጥሎ ትልቅ ወታደራዊ ሀይል የነበረው የትናንቱ ደርግ እንደ እንቧይ ካብ ሲናድ ተመልክተናል። አንባገነኖችመናገር እንጂ መስማት የማ ችሉ፤ ማየት እንጂ ማስተዋል የተሳናቸው በመሆናቸው እነሆ ዛሬም የወያኔ ዘረኛው ቡድን ህዝባ ላነሳው የነፃነትና የፍትህ ጥያቄ ያለ የሌለውን ወታደራዊ ሀይል በጠራራ ጸሀይ በማሰለፍ መቼውንም ያልተቻለ ውን ህዝብን በሀይል አሸማቆ ለመግዛት መከራውን ሲያይ ይስተዋላል። ለዚህም ነው ….. ከሌላው የሀገራችን ክልሎች ከፍ ባለ ሁኔታ የህዝባዊ እንቢተኝነት እየታየ ባለበት ጎንደርና አካባቢው በሰራዊት ማጥለቅለቅ የተያያዘው።

ለሚነሱ ህዝባዊ ተቃውሞዎችና ህዝባዊ የመብት ጥያቄዎች የሚሰጡት ምላሾች እስር፤ አፈናና ግድያ ከሆነ ህዝባዊ እንቢተኝነትን ማስከተሉ አይቀሬ ነው። በእስር ፤በአፈናና በግድያ እንዲሁም በሰራዊት ሀይል ህዝብን በማሸማቀቅ በስልጣን መቆየት የሚቻል ቢሆን ደርግም ከቤተ-መንግስት ባልወጣ፤ ወያኔም ዛሬ ከቤተ-መንግስቱ ባልተንፈልለሰ ነበር። ይህ ደግሞ ሊያስተምር በተገባ ነበር።

እስከ ዛሬ የትኛውም አንባገነን ስርአት በሚተማመንበት የወታደራዊ ሀይል አማካይነት የመንኮታኮቻቸውን ሰአት በአንድ ሰኮንድ ማዘግየት የቻለ እንደሌለ ሁሉ ወያኔም ያለ የሌለውን ወታደራዊ ሀይል ሲያርመሰምስ ውሎ ቢያድር ውድ ቀቱን በአንድ ሰኮንድ ማዘግየት እንደማይችል በተለይ እንቢ ለነፃነቴ፤ እንቢ ለሀገሬ… ብለን ለትግል የተነሳን ሀይሎች በመረ ዳት፤ ይበልጡኑ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተቀጣጠለ ያለውን ህዝባዊ እንቢተኝነት ይበልጥ እያሰፋን የጀመርነውን የነፃነት ጉዞ ከነፃነታችን አደባባይ ለማድረስ ሌት ተቀን የመስራት ሀላፊነታችናና መወጣት ይገባናል።

በጎንደር የሚታየውን የአልገዛም ባይነት ትንቅንቅ በሌሎች ክልሎችም በማቀጣጠል፤ በደብረወርቅ የታየውን የመምህራን የስራ ማቆም አድማ ወደ ሌሎች አካባቢዎች በማስፋት፤ እንደ ድምፃችን ይሰማ ሁሉ ተቃውሞን ወደ እንቢተኝነት በማሸጋ ገር …… ወዘተ የነፃነታችንን ቀን ለማቅረብ መከፈል የሚገባውን መክፈል ይገባናል።

በደርግ ል የተነሳው እንቢተኝነት እያየለ ሲመጣ ያሰለፈው ሰራዊት ወያኔን አጅቦ የደርግን ቀብር እንደቆፈረለት ሁሉ ዛሬም በወያኔ ላይ እየተቀጣጠለ የሚገኘው ህዝባዊ እንቢተኝነት እየጠነከረ በመጣ ቁጥር የደረደረው ሰራዊት የወያኔን ቀብር ቆፋሪ ከመሆኑ እንደማኢመለስ ከቅርብ ጊዜ ታሪካችን በመማር ነፃነታችንን ለማስከበር የጀመርነውን የእንቢተኝነት ትግል በ መ ላው የሀገራችን ክፍሎች በማስፋትና በማቀጣጠል አይቀሬውን የወ ኔ ቀብር ለማቅረብ በአንድነት የነፃነት ጉዞውን እንቀ ላቀል። የጀመርነው የነፃነት ጉዞ መቆሚያው የነፃነታችን አደባባይ መሆኑን በተግባር ከምናሳይበት ወቅት ላይ እንገኛለንና በአንድነት እንነሳ!!!!!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!!

The post “ጦር ሠራዊቱ ሕዝባዊ እምቢተኛነት ሲያይል የወያኔን መቃብር ይቆፍራል” – አርበኞች ግንቦት 7 appeared first on Zehabesha Amharic.

ሁለተኛው የትዊተር ዘመቻ ከመጋቢት 21 ወደ ሚያዝያ 19 ተዛዋረ!!!

$
0
0

‹‹የህዝብ ወኪሎችን በነጻ ከማሰናበት ያነሰ ብይን አንቀበልም!››
አርብ መጋቢት 18/2007

1508111_931747716876585_8049282190947484908_nበወኪሎቻችን የሽብር ክስ ‹‹የተከሰስነው እኛ ነን!›› በሚል መሪ ቃል መጋቢት 21/2007 ሊካሄድ የነበረው ሁለተኛው የትዊተር ዘመቻችን ወደ ሚያዝያ 19/2007 ተዛወረ! ይህ እንዲሆን የተወሰነው የውድ ወኪሎቻችን የብይን ቀጠሮ ባለፉት ቀናት በፍርድ ቤት ትእዛዝ ከመጋቢት 30 ወደ ሚያዝያ 30 እንዲሸጋገር በመደረጉ ነው፡፡

ለዘመቻው የምናደርገው ህዝባዊ ቅስቀሳ እና ዝግጅት እስከሚያዝያ 19 ባለበት እንደቀጠለ የሚቆይ ሲሆን ሰፊ የቅስቀሳ ጊዜ መኖሩም ዘመቻውን በተሻለ ስኬት ለመስራት ይበልጥ አመቺ እንደሚያደርገው የሚታመን በመሆኑ ሁላችንም የፌስቡክ ገጻችንን ፎቶ አሁን በተለጠፈው ፎቶ ዳግም በመቀየር በጀመርነው የቅስቀሳ ስራ ይበልጥ እንድንገፋበት አደራ እንላለን፤ ድልም ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለምና!

‹‹የህዝብ ወኪሎችን በነጻ ከማሰናበት ያነሰ ብይን አንቀበልም!››
ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!
ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

The post ሁለተኛው የትዊተር ዘመቻ ከመጋቢት 21 ወደ ሚያዝያ 19 ተዛዋረ!!! appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live