Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ሰማያዊ ፓርቲ በኢብኮ ከሚደረገው የምርጫ ክርክር ታገደ

0
0

• ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በኢብኮ ስቲዲዮ ከሚደረግው ቀረጻ ተባረዋል

ethiopia-blue-party-300x164ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ መጋቢት 18/2007 ዓ.ም ምሽት ኢብኮ ላይ ከሚቀርበው የ‹‹ግብርና እና ገጠር ልማት›› ላይ ሊያደርገው የኘበረው የምርጫ ክርክር ላይ እንዳይቀርብ መታገዱን የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል ለቀረጻ ወደ ኢብኮ ስቲድዮ ባቀኑበት ወቅት የድርጅቱ ምክትል ስራ አስካሄጅ አቶ ተሻለ ‹‹ባለፈው ያላሰባችሁትን የምርጫ ክርክር እድል ሰጥተናችኋል፡፡ በመሆኑም ዛሬ መከራከር አትችሉም›› ተብለው መባረራቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በሰአብአዊ መብት ዙሪያ ኢብኮ ላይ በቀረው የምርጫ ክርክር ላይ አንድ ፓርቲ ለመቅረብ ፈቃደኛ አለመሆኑን በመገልጹ በክርክር 5 ፓርቲዎች እንዲቀርቡ የሚደረግ በመሆኑ ሰማያዊ ፓርቲ እንዲቀርብ የተደረገ ሲሆን ዛሬ ምሽት በግብርና እና ገጠር ልማት ላይ የሚደረገው ክርክር ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ዕጣ የደረሰውና የፀደቀ ፕሮግራም ነው፡፡

በህገ ወጥ መንገድ ከቀረጻ ተባርሬያለሁ ያሉት ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ‹‹ኢብኮ በፕሮግራም የተያዘንንን የምርጫ ክርክር ላይ እንዳንቀርብ ያደረገው እሁድ በ15 ከተሞች ሰልፎች እንዳለን ስለለሚያውቅና የዛሬው ክርክር በየ አካባቢው ያለውን ህዝብ እንዳያነቃቃ ተፈልጎ ነው›› ብለዋል፡፡ ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት አክለውም ‹‹እስካሁን እየተደረጉት ባሉት ክርክሮች ሰማያዊ የኢህአዴግን ተግባራት እያጋለጠና ጠንካራ አማራጮችን እያቀረበ በመሆኑ ነው፡፡ ስለሆነም ኢብኮ ኢህአዴግን አግዞ ሰማያዊ ወደ ህዝብ እንዳይደርስ እያደረገ ነው›› ሲሉ ወቅሰዋል፡፡

The post ሰማያዊ ፓርቲ በኢብኮ ከሚደረገው የምርጫ ክርክር ታገደ appeared first on Zehabesha Amharic.


Health: ሪህ (Gout Arthritis)

0
0

(በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር)

የሪህ ሕመም የሚከሰተዉ ዩሪክ አሲድ የተባለው ኬሚካል በአጥንት መገጣጠሚያዎች ውስጥ በሚከማችበት ወቅት ነው፡፡ ይህ ዩሪክ አሲድ የተባለው ኬሚካል የሚገኘው ፕሮቲንን በዉስጣቸዉ ከያዙ ምግቦች ነው፡፡ የሪህ ችግር አንድ ጊዜ ከጀመረ በኋላ የመከላከያ ዕርምጃዎችን ካልወሰድን የመመላለስ ባህርይም አለዉ፡፡
rih
የአጥንት መገጣጠሚያዎች በተለይም በእግራችን የአውራ ጣት፣ በቁርጭምጭሚት፣በጉልበት፣በእጃችን የክንድ እና የእጅ መገጣጠሚያዎች ላይ ተከማችቶ ይገኛል፡፡

✔ የሪህ ህመም ስሜት ቀስቃሽ ሁኔታዎች
• ዉስጣዊ የሆኑ ህመሞች
• አልኮል መጠጦችን ማዘዉተር
• ፕሮቲን የበዛባቸው የምግብ ዓይነቶችን መመገብ (ስጋ፣ሽሮ የመሳሰሉት)
• የሰዉነት ቁስለት
• ድካም
• ጭንቀት
• በሃኪም የታዘዘን የሪህ መድኃኒት ማቆም ናቸዉ፡፡

✔ የሪህ ህመም ምልክቶች ምንድን ናቸዉ፡፡
• ከአንድ ወይንም ከዛ በላይ በሆኑ መገጣጠሚያዎች ላይ የሚኖር ኃይለኛ የሕመም ስሜት፡፡
• የመገጣጠሚዎች ማበጥ፣ መቅላት እና የሙቀት መጠን መጨመር
• ትኩሳት መኖር
• ብርድ ብርድ ማለት ናቸዉ

✔ ሪህ ተደጋግሞ እንዳይመጣ ምን ማድረግ ይገባል
• ፕሮቲን ያላቸውን ምግቦች በተለይም ቀይ የበሬ ሥጋ፣አሳ፣እንቁላል፣የመሳሰሉት ምግቦች መቀነስ ወይንም ለጊዜው ማስወገድ፣
• ውሃ በብዛት መውሰድ፣
• የአልኮል መጠጦችን አለመጠጣት፣
ከላይ የተጠቀሱት የሕመም ስሜቶች ሲሰማዎትም ሐኪምዎን ማማከር የኖርቦታል፡፡
ጤና ይስጥልኝ

The post Health: ሪህ (Gout Arthritis) appeared first on Zehabesha Amharic.

የእሳት ዲሞክራሲ ፣ የአበባ ሰብአዊነ እና የሰው ነፃነት እንደ ብረቱ ቅላት ነው

0
0

ይድነቃቸው ሰለሞን

በገላጣው ዘመን/ ያየ ከጨፈነ በማይተልቅበት

አንድ በሆኑበት/ ግልጡ እና ድብቁ  

ሰሙ ገፅ አይደለም ሸክም ነው ለወርቁ፡፡

(ግጥም፣ በእውቀቱ ስዩም፤ 2001፣127)

 

‹‹ሰው›› ለመኖር ሲታትር፣ ለማሰላሰል ሲጣጣር እና ለማግኘት ሲፈላሰፍ ለነገሮች የሚሰጠው ፍቺ ተስፋን የሰነቀ፣ መኖርን የሚያበረታታ፣ አብሮነትን የሚቀድስ፣ ሃሴትን የሚያላብስ በአጠቃላይ መልካም የሆነ እንጂ እኩይ ያልሆነ ሊሆን እንደሚጋባው እንስማማ፡፡ ካሂሊል ጂብራን በአንድ የግጥም ስንኙ ‹‹ጨለማ ፀሐይን ስትወልድ ተመልክተሃታልን››/ “Have you seen the darkness giving birth to the sun” ይላል፡፡ ጂብራንን ቀምሰን የሃገራችንን ባለቅኔ እናጣጥም፡፡ በህይወት ዑደት የተቋጨውን የብላቴን ጌታ ፀጋዬ ገብረመድህንን ሁሉን አቀፍ ለኢትዮጵያ ባህል እና ስነ-ፅሁፍ አበርክቶት ለማስታወስ ያህል ከሰፌዱ አንዷን ሰንደዶ በመምዘዝ እንጨዋወታለን- ለሙከራ ስለ መከራ፡፡ ዛሬ የምንስባት ሰበዝ በ1973 ታትሞ ለህዝብ ከደረሰው የግጥም መድብሉ ለመታወቂያነት የተመረጠ ነው፡፡ ይህም ባለቅኔው ለግጥሙ የሰጠውን ቦታ ያሳያል፡፡ በግሌ ይህ ግጥም የመድብሉ አቃፊ ግጥም እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ‹‹የገጣሚ ሞቱ ህይወቱ›› (እንዲል ጂብራን) በስራው ሁለገብነት፣ በስብዕናው እነከንየለሽነት፣ በኢትዮጵያዊነት ኩራት ወደር የማይገኝለትን (ክቡር) የዓለም ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህንን እናስበው፣ እናስተውለው፣ እንዘክረው ዘንድ ጥሩ አጋጣሚ ይሆናል፡፡ በዚህ ትንታኔ በእሳት-ወይ-አበባ የተነሱ ርዕሰ ጉዳዮች ከግጥሙ ጭብጥ ጋር ቀርቧል፡፡

ግጥሙ የሰው ልጅ ለነገሮች ስለሚሰጠው ትርጉም ይበይናል፡፡ ይህውም፣ ሰው ለነገሮች የሚያስቀምጠው ትርጉም መልካምነቱን የሚያጣው የውስጡን እውነት ሲገድሉት፣ ነፃነቱን ሲነፍጉት እና እምነቱን ሲነጥቁት ይሆናል፡፡ በተፈጥሮ የታደለው ‹‹ሰው›› በማህበረሰብ፣ በመንግስት፣ በባለዘመን የግል/የቡድን/የሃገር እውነቱን ሲቀማ ባለመታደል የውበት ዓይን ሲታወር፣ ባህረ-ሃሳብ ሲጨልም፣ እግረ-ህሊና ሲደድር ከግጥሙ እንመለከታለን፡፡ ከግጥሙ፣ ማህበራዊ ወይም/እና ተፈትሮአዊ እንስሳው ‹‹ሰው›› የሚያስቀመጠው ህገ-ደንብ ከተፈጥሮ ሲቃረን ውጤቱን እንገነዘባለን፡፡ ‹‹ሰው›› እምነቱን ሲነጠቅ ነገሮችን በይሁንታ እና በጥሩነታቸው ማስተናገድ እና መረዳት ይሳነዋል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ የውስጡን እውነት ሲከለከል ነው፤ በተለይም ተፈጥሮውን ሲሽሩበት፡፡ የማህበረሰብ ህግ ወይም የግለሰብ እይታ ከተፈጥሮ ሲጣላ ‹‹የሰው›› እሳቤ እና እይታ ጭለማ ይሆናል፡፡ ከመገንባት ማፍረስ፣ ከመመረቅ መርገም፣ ከመርዳት መበቀል፣ ከማስታረቅ ማናከስ፣ ከማበረታታት ማናናቅ የሚቀናው ይሆናል፡፡ እናም ብርሃናማነቱን ተነጥቆ ይታወራል፡፡ ተፍጥሮንም ማድነቅ ይሳነዋል፡፡

ባለቅኔው ‹‹ሌሊት›› ጨለማ እንዳይደል በቋንቋ ውበት ከሽኖ፣ በሃሳብ መጥቀት አርቆ፣ አይነኬ ሰማይን አቅርቦ ያስቃኘናል-ውበትን፡፡ የወርሃ መስከረምን ለዓይን ማራኪ ምድራዊ ውበት ከእኩለ ሌሊት ጨረቃ በክዋክብት ታጅባ ከምትፈነጥቀው ሰማያዊ ውበት ጋር ያነፃፅራል፡፡ በሌሊት ክዋክት እንደ ፀደይ ወቅት አበባ ‹‹በቀይ አደይ›› ያጥለቀልቁናል፣ ሰማይ ያማረ ምንጣፍ ተላብሶ ይፈካል፣ ተፈጥሮ በተፈጥሮ ያሸበርቃል፣ ምድር በጨረቃ ብርሃን ይደምቃል፡፡ በወረሃ መስከረም አጋማሽ ማለትም በእለተ መስቀል ከአዝዕርት እና ከአደይ አበባ በሚፈልቀው መአዛ ምድረ-ኢትዮጵያ ይታወዳል፡፡ በዚህ እለት ለደመራ፣ ጨረቃ የሸፈናትን ከል ገፍታ ስትፈልቅ እንደ እንቡጥ ፅጌሬዳ ናት፡፡ በመሆኑም ሰማይ ጨለማ ነው ማለት ውበትን ለማድነቅ አለመታደል፣ የምናብ አለመመጠቅ፣ በህሊናም አለመባረክ ነው፡፡ ይህን ነፀብራቃዊ ውበት ጨለማ አድረጎ መበየን መታወር ነው፡፡ ከብዙ መልካም ነገሮች መካከል ጥቃቅን ጉድፎችን አውጥቶ እንደ ማጉላት ያለ በእኩይነት የተቀነበቡ እውራን ጎራ ያስመድባል፡፡ ያለመታደል ነገር ሆኖ እንጂ ከክዋክብቱ የሚፈነጠቀው ብርሃን ከተለኮሰ ደመራ እንደሚወጣ እሳት ይፋጃል፡፡ የጨለማን ወበት አለመቀበል እቶን እያዩ እሳትነቱን የመካድ ያክል ያስነውራል፡፡

ይህ ገሃድ የወጣ ሃቅ ባለመታደል ካልተገለፀለት ግለሰብ ጋር ከጨራቃና ኮከቦች የፈነጠቀ ጨረረ ውበትን እንዳይመለከቱ የሆኑ አንድ ጉብል እና አንዲት ጉብል እናገኛለን፡፡ ስለዚህ በዚህ ክፍል ውስጥ የጨለማን እሳት የለበሰ አበባነት መካዱን ከላይ ባቀረበው ንፅፅር በሚገባ ጥበብ ካስረዳ በኋል በሚቀጥሉት ክፍሎች የጉብሉን እና የጉብሏን ውበት አለማስተዋል፣ በሃሳብ አለመታደል፣ በህሊና አለመጽዳት እንዴት እንደሆነ ይተነትንልናል፡፡

ጉብል በግለ ወግ ከጉብሉ ጋር ለመነጋገር አለመታደላቸውን፣ በማቀብ ስር እንዳሉም እንረዳለን፡፡ ሁለቱ ለየግላቸው በምኞት፣ በሰመመን፣ እና በጭንቀት ከመብሰልሰል በቀር በአብሮነት መወያየት አይችሉም፡፡ ይልቅስ ሁለቱን የሚገልፃቸው በዝምታ ውስጥ ያለ ዝምታ ይሆናል፡፡ ይህ ዝምታ ግን ሰላም የሰፈነበት ፀጥታ አይደለም፤ ለብየብቻ ሳግ እየተናነቃቸው በእንባ የሚርሱበት፣ በፍርሃት ውስጥ ተሸብበው ነፍስያቸውን የሚዘጉበት፣ የዋህነታቸው ያጎናፀፋቸውን የልጅነት እድሜ የሚያባክኑበት፣ በፍጡርነታቸው ፈጣሪ የቸራቸውን እውነታ የሚዘነጉበት፣ በአጠቃላይ መክሊታቸውን ሊያስጥል የታፈነ የውስጥ ሃሳብ እንደመሆኑ መጠን መስተ-ህልይ በርቅሶ ሊወጣ የሚችል አሰቃቂ ዝምታ ነው፡፡ ይህ ሁለቱን አበባ እንዳይሆኑ እሳትም እንዳይሆኑ ያግዳቸዋል፡፡ ጉዳዩን ከላይ ከተመለከትነው እውነታ ጋር ካናበብነው ውበት ማድነቅ ወይም ውበትን መቋደስ አለመቻላቸውን እንገነዘባለን- ሰማይን ጨለማ ነው ሲል አበባ እና እሳት የተጎናፀፈ ውበትን እንደካደው የምናብ ሰው፡፡

የማይወያዩት ሁለት ነብሶች አንድ ናቸው፡፡ ምስኪኖቹ ገፅ-ለ-ገፅ ተያይተው ልብ-ለ-ልብ ይናበባሉ፡፡ ለይቶ ሳይለያያቸው በእይታ እየገደባቸው፣ በይሉኝታ እንዳጠራቸው፣ በአሉ አሉ እንደለያቸው፣ ለይምሰል እንደከፈላቸው፣ ከብ ለካብ እንዳቆማቸው፣ እሳትም ሆነ አበባ እንዳላረጋቸው በቅፅበታዊ የዓይን ንግግር ሰመመናዊ ተግሳፁን ተረድታ የምር በውስጤ አርግዤሃለው ለማለት ጉብሏ ‹‹ሙት›› ብትለው በአንድነት ውስጥ ያሉ ሁለት ፍጡራን መሆናቸው ይገባዋል፡፡ እይታ ከሙት በላይ ምን ሊል ይችላል፡፡ ይህን ከዓይኗ የተረዳው ገጣሚ ግን ምላሷን በቂ ሆኖ አያገኘውም፤ የልብ ጉዳያቸው በአንዱ ጥጋት መነጋገር፣ መመካከር፣ እንደሚያስፈልገው ግን ደግሞ እንደተከለከሉ ግን ደግሞ አንድ እንደሆኑ … ግራ ቢገባው… በቃ ሁሉም ይቅር፤ ‹‹የወፎቹም ዜማ ይቅር››፣ ጨረቃንም ማድነቅ ይቅር ግን ደግሞ በይቅር ብቻ የሚቀር አይደለምና እንዴት ይቀራል፡፡ የማይያዝ፣ የማየጨበጥ ቢሆንበት፣የማያገኙት የማይተውት ቢሆንበት፣ የማይለዩት አብረው ያሉት ቢሆንበት ግራ ቢገባው … ‹‹ትዝታሽን ማሪኝ›› ሲል ይለምናታል፡፡

በይ ሕመምሽን ታረቂኝ

ሰቀቀንሽን ተማፀኚኝ

ሰመመንሽን ይቅር በይኝ

እምትምሪኝ ከሆነማ፣ ማሪኝ ፣ ትዝታሽን ማሪኝ  …

ጉብል በዓይኗ አልምርህም ብትለው ዘመን ተሻጋሪውን ቅኔ ይለቀዋል፡፡

ነገሩ አያድርስ ነው፡፡ ወይም የደረሰበት ብቻ የሚገባው ግን ሊገልፀው የማይችለው አይነት ነው፡፡ ሆኖም ባለቅኔው ሁላችንም ፅዋው እንዲደርስብን ያደርጋል፡፡ ደርሶኛል፡፡ በተመስጦ ግጥሙን ያነበብኩት ከሁለት አመት በፊት ሲሆን በደገምኩት ቁጥር ነብስያዬ አንደተረበሸች አለች፡፡ በጭንቅ ወልዳ የልጇን መጥፋት እንደገባት እናት ውስጤ በሃዘን ይጥለቀለቃል፡፡ ግን ደግሞ መቼም ግዜ ካለኝ ምናቤን ከልቤ አስታርቄ በመንፈስ የባለቅኔው ታሪክ ተጋርቸዋለው፡፡ የጥበብን የውበት ጥግ በቅኔው መንኮራኩር ተፈናጥጬ እታደማለሁ፡፡ እሳት እና አበባ እሆናለሁ፡፡

በአንድ ውጥን ያሉ ሁለት ነብሶች ቀርበው የጋራ ውጥናቸውን ለብቻ ከማሰላሰል በቀር ቀርበው ማውጋት አልቻሉም፡፡ ግና በአንድ አጋጣሚ በዓይን ስልምልምታ በተነጋገሩበት ቅፅበት ባለቅኔው የጉብሏ ችግሩን መረዳቷ ቢገባው ‹‹ሙት›› ብትለው ግራ ተጋባቶ ትዝታዋን እንድትምረው፣ ናፍቆቷን እንድታክመው፣ ሰቀቀኑን እንድታስታርቀው ቢለምናት ጉብል መልስ ጠፍቷት ዓይኗ ወጓን ቢገታ፣ ግንባሯ መሬት ቢመታ፣ እንባዋ በልውጣ አልውጣ ቢፈትናት … መልሷን ሳይሽት ከውጠ-ውስጠት በፈለቀ ስሜት ይንገበገባል፡፡ ትንታኔዬን ገትቼ …

ምነው ታድያን ድምፅሽ ራቀ?

ምነው ልሳንሽ ረቀቀ?…

የዓይንሽ ብረሃን ቀለስ አለየእንባ ወዝ እንደቋጠረ

ቃትቶ እንደተውተረተረ

የመከራ የጭንቅ የምጥ ስልባቦት እንዳቀረረ

የደም ወዝ እንደነዘረ

እንደተሰቀቀ ቀረ…

ላቀረበላት ‹‹የትዝታሽን ማሪኝ›› ጥያቄ መልሷ እንደፍላጎቱ ምህረት ሳይሆን አንጀት የሚያላውስ ፍርሃት ይሆናል፡፡ በጥያቄው የምትገባበት ያጣች የጉብሏ ነፍስያ ትንፋሽ ያጥራታል፡፡ የመግባቢያቸው በሯ የደረቀ እንባ አርግዞ፣ ሁለመናዋ በሰቆቃ ደንዝዞ ያማትራታል፡፡ የተረበሸ ውስጠቷ በእንባ መልክ የደም እንክብሎችን ለምድር ሲገብር ይታደማል፡፡ ሊያስተዛዝናትም ይሻል፡፡ እንባዋን አያበሰ አይዞሽ ሊላት ይመኛል፡፡ በዛውም ከአይኗ የሚፈልቁትን እሳታዊ ነበልባሎች ሊሞቅ ያስባል፡፡ አበባ የሆነውን እሳት ለውስጥ ህመሙ ፈውስ ሊፀበል፡፡ ቀርቧት የፊቷን ገፅ መዳበስ ባይችል እንኳን መንፈሳዊነትን በተላበሰ እስትንፋሱ ሊፈፅመው ይዳዳዋል፡፡ መለኮታዊ የሆነበትን ውበት በመለኮት ሊያሳካ፤ መንፈሱን ከመንፈሷ ሊያግባባ፤ ወደ ውስጠቷ ሊገባ፤ እሳት ሊሆን ወይ አበባ! ምክንያቱም ያለፍቅሯ በቀር እንባዋ ፍይዳው አይጠቅመኝም ብሎ ያምናል፡፡ እምነቱ ግን እውን አይሆንም፡፡ በዚህም መቃጠላቸው ቢበቃ ሲል ይደመጣል፡፡ ለቃጠሎ የዳረጉትን ፈጣሪውን፣ ማህበረሰቡን እና እድሉን አብዝቶ ያማራል፡፡ በልቡ የተቋጠረው ፍቅረ-ነገር ከሚችለውና ከአቅሙ በላይ ሲሆንበትም እንገኘዋለን፡፡ ቢበቃው ይመኛል፡፡ ፍላጎቱ ባይሳካ፣ ውጥኑ ግቡን ባይመታ፣ ምኞቱ ከምኞት ባያልፍ፣ አለመቻል ቢወርሰው፣ ህመም ቢተርፈው ቢበቃው ይመኛል፡፡ ከምኞት ፈቀቅ አይልም፡፡ የምኞት ምርኮ፣ የይሉኛታ ባሪያ፣ የፍርሃት አሽከር፣ የሰመመን ባላባት ነው፡፡

አረ ይብቃን መቃጠሉ፥ በዓይን ወላፈን መለብለቡ

ያለፈርጁ ያለባሕሉ፥ እሳት አይጭር ሰው በቀልቡ

ፍም አዝሎ ላይዘልቅ ልቡ፥

አጉል ምን አቀጣጠለን

በሰመመን ሟሟን እንጂ፥ በመውደድ ለምልሙ አላለን

ድባብ እንደራቃት ቆሌ

ባህር እንደገባ አሞሌ

እንዲያው በህልም አባይ ገነን፣ ለቅዠት መራወጥ ፎሌ

አረ ወዲያ ይብቃን  ይቅር

የኸ የአይን ብር ትር

ወዝ አይወጣው ድብን እርር…..

ጉብል ‹‹የምትታይ እንጂ የማትበላ›› የገነት ፍሬ ናት፡፡ እጣ ፋንታዋ በማህበረሰቡ እሳቤ ውስጥ የተቀነበበ፡፡ እሷን መንካት አይደለም መቅረብ የሚያስቀጣው፣ እሱን መቅረብ (በሌሎች) የሚያሳጣት  ነው፡፡ ሁለቱም ግን ይፈላለጋሉ፤ አንዳቸው ባንዳቸው ውስጥ ይነዳሉ፤ በአብሮነት ውስጥ ይጋያሉ፡፡ ሕልም አይከለከል፡፡ ምኞት አይታሰር፡፡ ተስፋ አይቀበር፡፡ እውነት አይገደል፡፡ ግን እሳት-ወ-አበባ መሆን አልቻሉምና ብቻቸውን በብቻነት ውስጥ ይጋያሉ፡፡ የከፈላቸውን ጋሬጣ አሽቀንጥረው አንደነታቸው ማሰሪያ ፍቅር መስራት አለመታደላቸው ያመዋል፡፡ በጋብቻ ከሆነ ለፅድቅ፣ በሴሰኝነት ከሆነም ለኀጢያት አለመታደላቸው ያንገበግበዋል፡፡ ይህን በህልም የሚደረግ እሩጫ፣ የሰመመን ውስጥ ፍጥጫ፣ የውስጥ ህመምን አለመናገር ‹‹መረገም›› ይለዋል፡፡ መረገማቸውም እውነትን በውስጣቸው ቀብረው የውሽት ከማስመሰላቸው አንፃር ይሆናል፡፡ እሷን ወግ ነው አጥሯ፤ እሱ ይሉኝታ ነው ከሉ፡፡ በማህበረሰቡ እንዳይታሙ ሲሉ የነፍሳቸውን እውነት ከፍሬነት ደጃፍ እንዳይደርስ ያጨነግፉታል፡፡ ይህም ብቻ አይደለም የህመማቸው ጥጋት፡፡ መዋደዳቸውን ለሽንገላ ደብቀው፣ መፋቀራቸውን በአደባባይ ክደው የማህበረሰቡ ውቃቢ አምላክ ያይብናል ሲሉ መፍራታቸው ይቆነጥጠዋል፡፡ ለማህበረሰቡ አካሄድ ሲባል ፍቅራቸውን መካዳቸው በመረገማቸው እና ባለመታደላቸው ይሆንበታል፡፡ የስቃያቸው ማብቂያ ግን አይሆንም፡፡ መተጣጣታቸው ማንነታቸውን ሲፈታተን ይዘልቃል፡፡ ያገባሉ፣ ይዳራሉ፣ ይሴሰኛሉ፡፡ የገደሉት መፈላለጋቸው ግን የገቡበት ይገባል፣ ያደሩበት ያድራል፡፡ ይፈትናቸዋል፡፡ የቱን ያህል ቢራራቁ፣ ምንስ ያህል ቢራቀቁ አንዳቸው ካንዳቸው ላይርቁ ነገር፡፡ ብቻ መሳቀቅ ነው፡፡ ሌላዋን እሱ እያቀፈ እሷን ይስላል፤ ሌላውን እሷ እያቀፈች እሱን ታያለች፡፡ ባንዷ አካል ጉብሉን ያግላል፤ ስሟን ከስሟ ያሳክራል፤ በማህፀኗ እሷን ይፀንሳል፤ ታቃፊዋን እቃው ያደርጋታል፤ ከሰውነት ያወርዳታል፤ ኃጢያት ይሰራባታል፡፡ ሁሉም በቁጭት ይለበልበዋል እና ጉብል ቢደርስብሽ ብታይው ይላል፡፡

ምነው ደርሶብሽ አይተሸው

የኔን ግፍ በሰው ውለሽው

የፍትወት ግብር ልትከፍይ የፈፀምኩትን ፈፅመሽ

በሰው አካል እኔን አቅፈሽ

በሰው ጭንቀት እኔን ፀንሰሽ፣

መውደዳቸውን ለወጉ አግዳ፣ ፍቅርን ለቧልት ክዳ፣ ለደስታ ሀዘናቸውን ሰንቃ፣ ለዘርየለሽ ገለባ አስታቅፋ፣ ለፍሬአልባ ወሬ ዳርጋ፣ ላይጠጣ የመነጨ ምንጭ አቅርባ፣ ላይፈጠር በተቀጨ ልጅነት ውስጥ፣ የማይወለድ ፅንስ አስቋጥራ፣ መኖራቸው ተንጉዳለች፡፡ ሕይወት መች ኬላ አላት፡፡ አትቆም ነገር፡፡ በቁዘማ ውስጥ ታልፋለች፡፡ ‹‹በተገማሸረ መስክ ውስጥ እንደሚብሰከሰክ ውሃ›› አለ ደራሲው፡፡ ሕይወት ሹሉክሉክ ትላለች፡፡ ስንቶቻችን ነን የሕይወታችንን ሽሉክሉኪት ለመታደም የሞከርን፡፡ እውነታቸውን በፍርሃት ውስጥ ሽሽገው፣ ፍቅራቸውን ለወግ ገብረው፣ ስሜታቸውን ለይሉኝታ ቸርችረው፣ እሳት ወይም አበባ፣ ፅድቅ ወይም ኩነኔ፣ ሳይደሰቱ ወይም ሳያዝኑ፣ በቁማቸው ሲቆዝሙ እድሜ ይሉት ነገር ድርስ ብሎባቸው እርጅት ቢሉ ምን ይውጣቸው፡፡ ‹‹ሾላ በድፍን›› እንደሆኑ ሳይተነፍሱት፣ ሣይናገሩት፣ እንዳማጡት ባክነውት አረፉት፡፡ ልጅነታቸውን ላይረባቸው እንዳልባሌ ቆሻሻ ደፉት፡፡ እንደተብከነከኑ ባከኑ፡፡ እንዲህ ሆኑ፡፡ ላይሆኑ ሆኑ፡፡ ጠቢቡ ሰለሞን ‹‹የከንቱ ከንቱ›› እንደለው ሆኑ፡፡

ልጅነትሽን ሳታካብች፥ ዕድሜሽን ምን ሳትሰሪበት

አባከንሽው ባከንሽበት፥

ልጅነቴን ሳላካብት፥ እድሜዬን ምን ሳልሰራበት

አባከንኩት ባከንኩበት፤

እሷን በውስጡ አዝሎ ላይ-ታች እንዳለ፤ ከልጅነት እስከ እውቀት እንደተብከነከነ፣ ምንም ቁምነገረ ሰይፈፅም ከእራሱ እንደተጣላ፣ ማንነቱ እንደተሳከረበት፣ የውስጡን ሰላም እንደ ተቀማ፣ በውበቷ እንደተሸበረ፣ እንዴት እንደሆነ ሳይገባው መባከኑ ግን ገባው፡፡ ልጅነቱን ከጎኑ አጣው፡፡

ተስፋና ምኞት ለፀጋሽ፥ ምዕጥንቱን በቻ ሳውቅበት

ነፍሴን ለነፍስሽ መስዋዕት፥ ግዳይ ስጥል ባደግኩበት

ሳንፈጠር በሞትንበት

ሳናብብ በረገፍንበት

ሳንጠና ባረጀንበት

አበባ ወይንም እሳት፥ መሆን ብቻ አጣንበት፡፡…

እንዳይሆን የለም፣ በመጨረሻ ውበትን ማድነቅ ይሳናቸዋል፡፡ ሕሊናቸው ባዶ ይሆንባቸዋል፡፡ ሁለመናቸው ከሰውነት ጎራ ይለያል፡፡ እናም ሰማይን ጨለማ ነው እንዳለው፣ አይኑ ስር ያለን እውነት እንደካደው፣ ውበትን ማገናዘብ እንደተሳነው፣ እግረ ሕሊናው እንደከረረበት ሰውዬ ይሆናሉ፡፡ ከምድር ሃሴት ይገለላሉ፡፡ አበባ ወይም እሳት መሆን እንደተመኙ፣ ስለመቀራረብ ዘውትር እንደተብሰለሰሉ፣ ስለአብሮነት እንዳለሙ፣ ለፍሬ ለመብቃት እንደታተሩ፣ ሳይሳካላቸው ይቀራሉ፡፡ ይባክናሉ፡፡ ባካናዎች ይሆናሉ፡፡

እናም የግጥሙ ማሰሪያ የሚሆነው የታፈነ እውነት ገዳይነት፣ የተደበቀ ማንነት አጥፊነት፣ ለወግ እና ለይሉኛታ የሚደበቅ ሃቅ እኩይነት፣ የድፍረት ማጣትን እዳነት፣ የአስመሳይነትን ዋጋቢስነት፣ ….ሌላም….ሌላም…ሌላም ሊሆን ይችላል፡፡ ማንነትን ከማጣት ቅጣት፣ እውነትን ካለመፈለግ መዓት፣ በሃሰት ከመሸሸነጋገል ሃጢያት እና ውበትን ካለማድነቅ ክፋት ይሰውረኝ፣ ይሰውራችሁ፡፡ ካልሰወረን ግን ማረፊያችን ወይም እርግማን ነው፣ ወይም አለመታደል ነው፣ ወይም ፍርሃት ነው፡፡

በውልደት እና ሞት መካከል በታጠረች መኖራችን ውሰጥ ተፈጥሮ እኩልነትን እንዳልነፈገን ይሰማኛል፡፡ ተፈጥሮ የመልካምነት ተምሳሌት ትሆናለች፡፡ ለምሳሌ፣ ሰብዓዊነት ውበት አለው፡፡ እንደ አበባ ነው፡፡ ለምሳሌ፣ ዲሞክራሲ ውበት አለው፡፡ እንደ እሳት ነው፡፡ አበባ እሳትም ነው፡፡ ሰብዊነት ዲሞክራሲም ነው፡፡ እሳትም አበባ ነው፡፡ ዲሞክራሲም አበባ ነው፡፡ ሁለቱን አቃፊ ሶስተኛው ነፃነት፣ ነፃነት፣ ነፃነት ነው፡፡ እንደ ብረቱ ቅላት ነው፡፡

Comment

The post የእሳት ዲሞክራሲ ፣ የአበባ ሰብአዊነ እና የሰው ነፃነት እንደ ብረቱ ቅላት ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

“ከትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ለኢትዮጵያ በጎ ነገር ይመጣል ብሎ ማሰብ ከዕባብ ዕንቁላል እርግብ ይፈለፈላል ብሎ ማመን ነው”–ሞረሽ ወገኔ

0
0

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት
አርብ መጋቢት ፲፰
 ቀን ፪ሺህ፯  ዓ.ም.           ቅፅ ፫ ፣ ቁጥር ፲፫

ሠሞኑን በትግሬ-ወያኔ፣ በግብፅ አረብ ሪፑብሊክ እና በሱዳን እስላማዊ አገዛዝ መካከል በአባይ ወንዝ የውኃ አጠቃቀም ላይ የሚያተኩር የጋራ የሥምምነት ሠነድ ተፈርሟል። የሥምምነቱ ሠነድ ለሕዝብ ይፋ የሆነው ማክሰኞ መጋቢት ፲፭ ቀን ፪ሺህ፯ ዓ.ም. (Tuesday March 24, 2015)ነው። ሆኖም የሥምምነት ሠነዱ የወጣበት የካቲት ፳፮ ቀን ፪ሺህ፯ ዓ.ም. (Thursday March 5, 2015) እንደሆነ በሠነዱ ራስጌ ላይ የሠፈረው ጽሑፍ ያመለክታል (ምንጭ፦ http://aigaforum.com/documents/Final-full-text-of-egypt-sudan-ethiopia-agreement-on-nile-use.pdf)። ሥምምነቱን የተፈራረሙት የሦሥቱ አገዛዞች ገዢዎች እስካሁን ድረስ ዘግይተው ሠነዱን ለሕዝብ ይፋ ያደረጉበት ምክንያት ምናልባት ከሚገዟቸው አገሮች ሕዝብ ሊነሣባቸው የሚችለውን ተቃውሞ ለማለዘብ ታስቦ ይሆናል፣ ወይም ሌላ የተደበቀ አጀንዳ ይኖራቸዋል። ወጣም ወረደ ሠነዱ ለእያንዳንዱ አገር ሕዝብ፣ በተለይም ለኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የሚያመጣው በረከትም ሆነ የሚያወርደው መቅሠፍት ካለ ያንን በጥልቀት መመርመሩ እና ተገቢውን እርምጃ መውሰዱ የእያንዳንዱ ኃላፊነት የሚሠማው ዜጋ ግዴታ ነው።

Moreshየትግሬ-ወያኔ አገዛዝ በአባይ ወንዝ የመብት ጥያቄ ላይ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሉዓላዊነት አሣልፎ የሠጠው ገና ወደሥልጣን ከመጣ ሦሥት ዓመት ሣይሞላው ነው። በሰኔ ፳፬ ቀን ፲፱፻፹፭ ዓ.ም.  (Thursday July 1, 1993) የያኔው የትግሬ-ወያኔ የሽግግር አገዛዝ ፕሬዘዳንት መለስ ዜናዊ ካይሮ ድረስ ሄዶ ከያኔው የግብፅ አምባገነን ገዢ ሆስኒ ሙባረክ ጋር አንድ ሠነድ ተፈራርሟል (ምንጭ፦ http://ocid.nacse.org/tfdd/tfdddocs/521ENG.pdf)። የዚያ ሥምምነት ዓላማ ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ እና በገባር ወንዞቹ ላይ ያላትን ተፈጥሯዊ እና ሉዓላዊ መብት አሣልፎ የሚሠጥ መሆኑን በተለያዩ ባለሙያዎች እና ፖለቲከኞች የተተቸበት ጉዳይ ነው።

ሆኖም ከአራት ዓመታት በፊት ሟቹ የትግሬ-ወያኔዎች መሪ መለስ ዜናዊ በድንገት ተነስቶ «አባይን እንገድባለን» ሲል በኢትዮጵያውያን መካከል ያልተጠበቀ መከፋፈል ተፈጠረ፦ ከፊሉ «የዚህ ግድብ መገንባት ተገቢ ነው፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ይጠቅማል፣ ወያኔንም በገንዘብ እና በማናቸውም መንገድ ልንደግፈው ይገባል» ብሎ ተነሣ። ከፊሉ ኢትዮጵያዊ ደግሞ «የትግሬ-ወያኔ ለኢትዮጵያ የሚያስበው መልካም ነገርም ሆነ የሚያመጣው ጠቃሚ ነገር የለውም፤ እንዲያውም ለአሁኑ ብቻ ሣይሆን ለተከታዮቹም ኢትዮጵያውያን ትውልዶች የማይነቀል እና የተወሣሠበ የችግር ነቀርሣ ይተክላል» ብለው አምርረው ተቃወሙ። በዚህ መካከል ገለልተኛ ሆነው ከሁለቱም ወገን የሚወረወረውን የቃላት ጦርነት በትዝብት የሚከታተሉም አይጠፉም። ወጣም ወረደ መለስ ዜናዊ ያንን ያልተጠበቀ ቃሉን ከሠጠ ከዓመት በኋላ ቅዳሜ መጋቢት ፳፬ ቀን ፪ሺህ፫ ዓ.ም. (Saturday April 2, 2011) በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር አቅራቢያ በ15 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የግድቡን ሥራ አስጀመረ።

ሀገር ወዳድ እና ሃቀኛ ኢትዮጵያን አስቀድመው እንዳስጠነቀቁት፣ በግድቡ መገንባት ሥም የትግሬ-ወያኔ ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጥቅሞችን አካበተበት፦ በመዋጮ ሥም በቢሊዮን ዶላሮች የሚቆጠር ገንዘብ ወደካዝናው አስገባ፣ በፖለቲካው ረገድ «ተቃዋሚ ነን» የሚሉትን ለመከፋፈል እና ለማዳከም ተጠቀመበት። ነገር ግን የግድቡ ሥራ በትክክል ምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ ሣይታወቅ ይኼው አራት ዓመት ሊሞላው ጥቂት ቀናት ቀርቶታል። የግድቡ ሥራ ከመጀመሪያውም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለታሪካዊ ጠላቶቿ አሣልፎ ለመስጠት መሆኑ አያጠራጥርም። ስለዚህ የትግሬ-ወያኔ ኢትዮጵያን አፈራርሶ፣ ዜጎቿን ከፋፍሎ፣ ግዛቷን ለውጭ ኃይሎች የመቸብቸብ የመጨረሻውን ግቡን ሣያሣካ እንደማያርፍ ማሰብ የማይችል ኢትዮጵያዊ ካለ የአዕምሮው ጤንነት የተቃወሰ ብቻ ነው።

ይህ በዚህ እንዳለ፣ የትግሬ-ወያኔዎች የተፈጥሮ ባሕሪያቸው የሆነውን የአገር ክህደት ድርጊታቸውን በመቀጠል፣ ባለፈው ሰኞ ዕለት መጋቢት ፲፮ ቀን ፪ሺህ፯ ዓ.ም. (Monday March 23, 2015) የሠሞኑን የሥምምነት ሤራቸውን ሠነድ በድረ-ገፃቸው ላይ ይፋ አርገዋል (ምንጭ፦ (http://aigaforum.com/documents/Final-full-text-of-egypt-sudan-ethiopia-agreement-on-nile-use.pdf)። ስለሆነም «በዚህ የሤራ ሠነድ ካሉት አንቀፆች በተለይ የኢትዮጵያን እና የኢትዮጵያውያንን ኅልውና በእጅጉ የሚፈታተኑት የትኞቹ ናቸው?» ብሎ በጥንቃቄ መመርመሩ ተገቢ ነው። በተለይ፦

·               አንቀፅ 3፦ ፍትኃዊ የውኃ አጠቃቀም መርሆ (III. Principle of Equitable and Reasonable Utilization)

·               አንቀፅ 4 ሌላውን አካል ያለመጉዳት መርሆ (IV. Principle of Not to Cause Significant Harm)

·               አንቀፅ 5 የግድቡን ወኃ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመሙላት ስለሚያስፈልገው የትብብር ሥራ (V. Principle to Cooperate on the First Filling and Operation of the Dam)

በሚሉት አንቀፆች ላይ ኢትዮጵያውያን በጥልቀት ተወያይተው ብሔራዊ መግባባት እና የጋራ አቋም ላይ መድረስ ይገባቸዋል። እኒህ አንቀፆች እርስ በእርሣቸው በሚቃረኑ፣ በተድበሰበሱ እና የኢትዮጵያንም የወደፊት ኅልውና አደጋ ላይ በሚጥሉ አረፍተተገሮች የታጨቁ ናቸው። ስለዚህ እኛ ኢትዮጵያውያን በሠከነ መንፈስ፣ ሣንዘላለፍ፣ ነገሮችን በጥልቀት እየመረመርን ለችግሩ መውጫ መንገድ መፍትሔ የሚሆኑ ኃሣቦችን ማፍለቅ ይጠበቅብናል። 

የዚህ የአዲሱ ሥምምነት ዓላማው በግልፅ፦ «እኛ ወያኔዎች በኢትዮጵያ ላይ ማንም አዛዥ-ናዛዥ የሌለብን ገዢዎች ነን፣ ምን ታመጣላችሁ!» ለማለት ነው። ለነገሩ ከትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያን መልካም ነገር ይመጣል ብሎ ማሰብ ከዕባብ እንቁላል እርግብ ይፈለፈላል ብሎ የማመን ያህል ቂልነት ነው። ስለሆነም ኢትዮጵያውያን በአንድነት ቆመን ተገቢውን የተግባር ምላሽ ልንሠጥ ይገባል። ይህንን ማድረግ ካልቻልን ግን የዚህ ትውልድ ኢትዮጵያውያን ከአገር አፍራሹ እና ሻጩ የትግሬ-ወያኔ ባልተለየ ከሃዲዎች በመሆናችን በታሪክ ከተጠያቂነት አናመልጥም። 

ኢትዮጵያ በታማኝ እና ቆራጥ ልጆቿ መስዋዕትነት ለዘለዓለም ፀንታ ትኖራለች!

The post “ከትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ለኢትዮጵያ በጎ ነገር ይመጣል ብሎ ማሰብ ከዕባብ ዕንቁላል እርግብ ይፈለፈላል ብሎ ማመን ነው” – ሞረሽ ወገኔ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢትዮጵያና ዐባይ –ግብፅና እስልምና!! –አንተነህ ሽፈራው

0
0

መጋቢት 19 ቀን 2007 ዓ.ም (March 28, 2015)

Blue Nile. . . ይኩኑ አምላክ የኢትዮጵያን ማዕከላዊ ሥልጣን ከዛጉኤ ሥረዎ-መንግሥት (ከላስታ) እ.ኤ.አ 1270 ዓ.ም ነጥቀው ወደ ሸዋ ሲወስዱ የመጀመሪያው እቅዳቸው በሁሉም የኢትዮጵያ የግዛት ማዕከሎች ያሉ ክርስቲያኖችን ሚዛናዊ በሆነ መንገድ ሃይማኖታዊ ግልጋሎት የሚሰጥ አባት/አቡን/ ይፈልጉ ስለነበር ትኩረታቸውን ወደ ግብጽ አደረጉና የዛን-ግዜውን የግብፅን ፈርሆን/ንጉሥ/ ሱልጣን ባይባርስን እ.ኤ.አ በ1272 በይፋ ቢማጸኑም ሱልጣን ባይባርስ ግን የክርስትና ሃይማኖት መኖርን አለመፈለጉ ብቻ ሳይሆን የክርስቲያን ኑባ ሥረ-ወመንግሥትን ጭራሽኑ ለማውደም በከፍተኛ ዘመቻ ላይ ነበርና የይኩኑ አምላክን ተማጽኖ ሊያስተናግድ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ይኩኑ አምላክም (ከብዙ ቆይታ በኋላ) ፊቱን ወደ ሶሪያ በማዞር አባትነቱን ለሶሪያው ጃአኮቢት ሰጡ. “Baybars, was engaged in the conquest of the Crusaders’ last strongholds in the Holy Land. But he also directed a campaign aimed at destroying the Christian Kingdom of Nubia] …-—[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—–

 

The post ኢትዮጵያና ዐባይ – ግብፅና እስልምና!! – አንተነህ ሽፈራው appeared first on Zehabesha Amharic.

ዘመናዊ ባሪያ ፍንገላ በኢትዮጵያ (ነፃነት ዘለቀ – ከአዲስ አበባ)

0
0

በታሪክ ትምህርት የሚወሳ “የባሪያ ፈንጋይ ሥርዓት” የሚባል ማኅበረሰብኣዊ ዕድገት የወለደው ጥንታዊ ሥርዓት ነበር፡፡ ያ ሥርዓት በወቅቱ በሰው ዘር መካከል ትልቅ የልዩነት ቋጥኝ ፈጥሮ አንዱን ጌታ ሌላውን ሎሌና ከዚያም አልፎ የጊዜ ማሳለፊያና የመዝናኛ ዕቃ በማድረግ የማይፋቅ ጠባሳ አስቀምጦ ያለፈ ሥርዓት ነው(ሰውን ከአንበሣና ከነብር እያታገሉ በሰው ስቃይ የሚደሰቱ መኳንንትና መሣፍንት ነበሩ)፡፡ ለዚህ ሲያስቡት እንኳን ለሚዘገንን የታሪክ ስብራት አሜሪካ ኅያው ምሥክር ናት – ምንም እንኳ ነገሮች በተወሰነ መልክና ባልተጠበቀ መንገድ ቅርጻቸውን ለውጠው የጉዳቱ ሰለባዎች ለይስሙላም ቢሆን አሁን አሁን መንበረ ሥልጣን የጨበጡ ቢመስሉም የጓዳ ጎድጓዳው ታሪክ አሁንም ብዙ የተለወጠ አይመስልም – በጥቁርና በነጭ የሚታየው የዘር ልዩነት አሁንም ድረስ አልጠፋምና፡፡ አፍሪካውያንና ካሬቢያውያን በተለይም ጋናንና ቤኒንን የመሳሰሉ የባሪያ ንግድ ይጧጧፍባቸው የነበሩ ሀገሮችም ቋሚ ምሥክሮች ናቸው፡፡ የእነኩንታኩንቴ ታሪክ መቼም ቢሆን በኅያውነት ይቆያል፡፡ በኢትዮጵያም እነግንደበረትና እነሰሜን ሸዋ፣ እነቦንጋም ይመስክሩ፡፡ ቋንጃ መቁረጥ፣ የሰውን ልጅ ዛፍ ሥር ኮልኩሎ በወፈረና በከሳ፣ በዕድሜ በገፋና ባልገፋ፣ ባጠረና በረዘመ፣ ከብት ይመስል ጥርሱን በሸረፈና ባልሸረፈ … እየተባለ የሰው ልጅ እንደእንስሳና እንደአሞሌ ጨው በገንዘብ ወይም በዓይነት ይሸጥ ይለወጥ ነበር፡፡ ያ እንግዲህ ዱሮ ነው፡፡ አልፏል፡፡ መልኩን ቀይሮ በኢትዮጵያችን ሊያውም ሰላምን፣ ፍትህን፣ ነፃነትን፣ እኩልነትንና ዴሞክራሲን ከአንደበቱ በማይነጥለው የሕወሓት መንግሥት በዘመናዊ መልኩ አሁንና ዛሬ እውን ሲሆን ግን ምን እንላለን? “ጭቆናና መድሎ አስመርሮኝ ሕዝቤን ነፃ ላወጣ ለትግል በረሃ ወጣሁ” የሚለው ሕወሓት ጥንት የሞተን የባሪያ ፈንጋይ ሥርዓት ነፍስ ዘርቶበትና አቀንቃኝ ሆኖ በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ብቅ ሲል በተለይ የድርጊቱ ሰለባዎች ምን ይዋጠን? አሣዛኝ ድርጊት በሀገራችን እየተፈጸመ ነው፡፡ እመለስበታለሁ፡፡

በምሥጋና መጀመር ነበረብኝ፡፡ ይቅርታ፡፡ ብዙም አልረፈደብኝም፡፡

በዚህን ሰሞን “ኑሮ በአዲስ አበባ” በሚል ርዕስ አንድ መጣጥፍ ማቅረቤን ተከትሎ ከወትሮው ለዬት ባለና እኔንም ባስገረመኝ ሁኔታ ብዙ አንባቢያን ልባዊ እርካታቸውን በመግለጽ በግል አድራሻየ መይለውልኛል፡፡ ለሁሉም በወቅቱ መልስ ሰጥቻለሁ፡፡ ግን በዚህ አጋጣሚ ለሁሉም በሁሉም አንባቢያንና በድረገፆቻችን ስም በድጋሚ ላመሰግናቸው እፈልጋለሁ፡፡ ከውድ ጊዜያቸው ተሻምተው ያን ብሶት-ወለድ ረጂም መጣጥፍ በማንበባቸውና በኑሯችን ከምር አዝነውም ያን የመሰለ ነፍስና ሥጋን የሚያለመልም የሞራል ድጋፍ ከዚያቺው ዕንቁ ጊዜያቸው ሰውተው በመላካቸው አሁንም ምሥጋናየ ድንበር የለውም – ጫት ቤቶችንና መጠጥ ቤቶችን ስታዘብ በኛ ሀገር በኮንቴይነር አሽገን ወደዓለም የጊዜ ገበያ ኢክስፖርት ልናደርገው የምንችለው “ጊዜ” በብዛት እንዳለን ብገነዘብም በውጭ ሀገራት ለሰላምታ እንኳን ጊዜ እጅግ ውድና ብርቅ እንደሆነ እሰማለሁ – ለዚህም ይመስላል ሰዎች በእግር እየተጓዙ በተመሳሳይ ቅጽበት ስልክ የሚያናገሩት፣ ምግብ የሚመገቡት፣ ጽሑፍ የሚያነቡትና… በአካባቢ የሚከናወንን ነገር የሚቃኙት፡፡ አንዲት ደቂቃ ወርቅ ናት፡፡ እንደውነቱ ከሆነ ጽሑፍ መጻፍ ከጀመርኩ ጊዜ አንስቶ ጽሑፌን በማንበብ ይህን ያህል በሀገሩ ጉዳይ ልቡ የተነካ አንባቢ ገጥሞኝ አያውቅም፡፡ በኔ የጋዜጠኝነት ዕውቀት የአንድ ሰው አጸፋ(feedback) በመቶ ሰው ይመነዘራል፡፡ ስለዚህም እስካሁኒቷ ቅጽበት ብቻ በጎ አስተያየታቸውን የላኩልኝ 15 ሰዎች 1500 ሰዎችን እንደሚወክሉና አጻጻፌንና መልእክቴን ክፉኛ ነቅፎ የወቀሰኝ አንድ ሰው ደግሞ በሌላኛው ጎራ 100 ሰዎችን እንደሚወክል በወያኔያዊ ቋንቋ ግንዛቤ ወስጃለሁ፡፡ የዚህኛውን ሰው አስተያየት ለፍርድ እንዲያመች በመጨረሻው ላይ እንዳለ አስቀምጠዋለሁ፡፡ የሌሎችን ግን ሙያ በልብ ነውና በኔው ይቅር፡፡ ግን ግን አይዞን፤ እንደጨለመብን አንቀርም፡፡ የተበተነው የሚሰበሰብበት፣ የተራበ በልቶ የሚጠግብበት፣ ጠግቦ የሚዘል አደብ የሚገዛበት፣ ፍትህ ርትዕ የሚሠፍንበት፣ ፍቅርና መተማመን የሚናኝበት፣ የእህል በረከት የሚበዛበት፣ … እውነተኛ የመኖሪያ ድባብ በሀገራችን በጣም በቅርቡ ይፈጠራል፡፡ እንዲህ ይታየኛል፡፡ ገደሉን ጨርሰን ጫፍ የደረስንም ይመስለኛል፡፡ መመኪያየ ግን ኢትዮጵያን ፈጥሮ የማይረሣት አምላከ ኢትዮጵያ ወአምላከ ኩሉ ዓለም እንጂ ሰው አይደለም፡፡ተስፋችን እሱ ነው፡፡

ድረ ገፆችን በሚመለከት ሁሉንም ማመስገን እፈልጋለሁ፡፡ እነሱ ባይኖሩ የነፃነት ትግላችን በብዙ ማይሎች ወደኋላ ይቀር ነበር፡፡ ችግራችን እንዲሰማ፣ የሌላው ዓለም ሕዝብም እንዲያውቅልን፣ የነፃነት አርበኞች እንዲጠራሩና እንዲወያዩ … በማድረግ ረገድ እየከፈሉ ያሉት ከፍተኛ መስዋዕትነት በታሪክም በፈጣሪም ዘንድ ትልቅ ዋጋ የሚያሰጣቸው ነው፡፡ አምላክ ይጠብቃቸው፡፡

ይህን ስልም ከነህፀፃቸው ነው፡፡ ዓለማችን ምሉዕ በኩልሄ አይደለችም፡፡ ፍጹምነት የለም፡፡ ማንም በምንም ዓይነት መለኪያ ፍጹም አይደለም፡፡ ከዚህ ፍጹምነትን ከመሻት አኳያ ማናችንም ብንሆን በየሥራችን እንዳንታበይ ወንድማዊ ምክሬን መሰንዘር እወዳለሁ፡፡ ያጠፋን ሳይመስለኝ የምናጠፋበት ጊዜ ብዙ ነው፡፡ ዐውቀን የምናጠፋበት ጊዜም እንደዚሁ አለ፡፡ ቂም የምንቋጥር፣ በቡድን ስሜት በመገፋት በግል ያልበደሉንን የምናሣዝን፣ መቻቻልን የማናውቅ፣ በዱሮ በሬ የምናርስና ከረሜላ እንደከለከሉት ሕጻን በቀላሉ የምናርኮፍ፣ ወዘተ. አለን፡፡ ሰዎች እንደመሆናችን አመንነውም ካድነውም እንሳሳታለን፡፡ እኔ በበኩሌ እንደዚህ ነኝ፡፡ እሳሳታለሁ፤ በስህተቴም እጸጸታለሁ፡፡ ይቅር በሉኝ ብዬም የበደልኳቸውን ሰዎች ከልብ በመነጨ ስሜት እለምናለሁ፡፡ እንዲያ ስንሆን ይመስለኛል የሰው ልጅን የዕድገት መሰላል ወደላይ የምንወጣው፡፡ እንዲህ ካልሆን ታጥቦ ጭቃ እንሆናለን፤ ንግግራችንና ተግባራችንም ለዬቅል እንደሆነ ይቀራል፡፡ በንግግር ብዙዎቻችን እጅግ መሳጭ ነን – በምግባር ግን ያን ያህል አንሆንም፡፡ በጸጸትና በንስሃ፣ በመደማመጥና በመግባባት በተመሠረተ ይቅር መባባል መንፈሣዊ ፈውስን ካላገኘን በመጎሻመጥና በመገፈታተር፣ በትዕቢትና በትምክህት የትም አንደርስም – ምናልባት የነዚህ ነገሮች አባትና የክፋት አበጋዝ ወደሆነው የዲያብሎስ ቤተ መንግሥት ልናመራ እንችል ይሆናል – ያ ደግሞ ብዙ ልፋትና ድካም የለበትም፡፡ ቂምንና በደልን ሠርዞ (ልብ በል – ረስቶ አላልኩም! የተረሣ ይታወሳልና፡፡) በአንተ ትብስ በአንቺ ትብሽ በአዲስ መልክ ፍቅርንና መዋደድን መመሥረት ግን ከባድ ከባድ ቢመስልምና ቢሆንም ይቻላል – ባሕርያዊ እልኸኝነትንና ዕብሪትን ማሸነፍ ከጦርነቶች ሁሉ ከባዱ ይመስለኛል፤ ጽጌረዳ ታምራለች፤ ይቅር ባይነትም ሃሤትን የሚያረብብ ዕፁብ ድንቅ ነገር ነው – ወደአምላክም ያስጠጋል፤ ሁለቱም ግን እሾሃማ ናቸው – በቀላል አይገኙም፤ ጽጌረዳዋ እጅን የሚወጋ ጦረኛ እሾህ፣ ይቅርባይነትም ስሜትን የሚፈታተን መግነጢሳዊ ኃይል አላቸው፡፡ እስከማውቀው ድረስ ትዕቢትና እልኸኝነት ማንንም አዋጥተው አያውቅም፡፡ ስሙን ቄስ ይጥራውና ያን የአዳምና የሔዋንን ቀንደኛ ጠላትም ወደታችኛው ዓለም(the netherworld) ከገነት አውጥቶ ያሽቀነጠረው ይሄው ትዕቢት ነው፡፡
ሳልጠቀስ የማላልፈው ወቀሳ አለኝ፡፡ ይህ ወቀሳየ ደግሞ የኔ ብቻ ሣይሆን የብዙ ጸሐፍት መሆኑን እረዳለሁ፡፡ የችግር ትንሽና ትልቅ የለም ብዬ ስለማምን ይህንንም በመጠኑ ማንቀራበጡ አይከፋም ባይ ነኝ – ተገቢ ትኩረት ያልተሰጠው ትንሹ ችግር ነው አድጎ ትልቅ እሚሆን – “እማዬ፣ ምነው በዕንቁላሌ በቀጣሽኝ!” የሚለውን ሥነ ቃላዊ ብሂል እናስታውስ፡፡ አንድን ችግር ሳይብስበት መግለጡ ለመፍትሔው በግማሽ እንደመቅረብም ይመስለኛል፡፡ ‹ኑ እንዋቀስ‹ አልነበር የሚል ያ አላበሳው ተሰቅሎ የሞተ የዓለም መድሓኒት? ብንዋቀስ ምን ወጪ እናወጣለን? ተዋቅሰን ብንታረቅና የሰይጣንን ቀንድ ብንሰብር ተጠቃሚዎች ነን፡፡ ጥቅምን ደግሞ በግድ ከማቴሪያላዊ ጎኑ ብቻ ማየት የለብንም፡፡ እንደችግር ሁሉ የጠብም ትንሽና ትልቅ የለውም፡፡ ለምሳሌ የኔን ተግባርና ጠባይ ልትንቅ ትችላለህ – እኔን ግን ልትንቀኝ አይገባም፡፡ ነውር ነው፡፡ ኃጢኣትም ነው፡፡ እንዳንተው ሰብኣዊ ፍጡር ነኝና አንተ ባንተ ላይ እንዲያደርጉብህ የማትወደውን ነገር ሁሉ በኔ ላይ ልታደርግ አይገባም – ኮንፊውሸስ ተናገረው፣ አሊጋዝ ደገመው እውነቱ ይሄው ነው፡፡

ዝም ብዬ ሳስበው አንዳንድ ድረገፆች ምን እንደሚፈልጉ የሚያውቁ አይመስሉኝም፡፡ የሚፈልጉትን ነገር እንዳለማወቅ የመሰለ አስከፊ በሽታ ደግሞ የለም፡፡ ጅል ባህል ሆኖባት ሣይሆን አይቀርም ያገሬ ሣዱላ በፍቅር የነሆለለላትን ጉብል ንቃ (ባህሉን ስለሚያውቅ ሆን ብሎ እንድትወደው በማሤር የናቃት መስሎ የሚጀነንባትን ጭምር መሆኑን ልብ ይሏል) የሚንጠባረርባትንና የሚጠላትን እንደምታፈቅር ሁሉ አንዳንድ የድረገፅ አዘጋጆችም በፍቅር የሚንሰፈሰፍላቸውን ወገናቸውን ያለመለየት ችግር አይባቸዋለሁ፡፡ በበኩሌ ምን ስጽፍ በየትኞቹ እንደሚወጣና በየትኞቹ እንደማይወጣ አስቀድሜ ዐውቃለሁ – ባብዛኛው፡፡ ይህ ዓይነቱ መለስተኛ ልዩነት የሚለመድ ነው – በቂ ምክንያት ኖረውም አልኖረውም በበኩሌ ለምጀዋለሁና አንዳንዶች ነሸጥ አድርጓቸው ፊት ሲነሱኝ ማቅ አልለብስም፡፡ ደግሞም – በሚገባ አምናለሁ – የዜጎች ሁሉ አስተሳሰብና አመለካከት በግድ አንድ መሆን የለበትም፤ ልዩነት ይኖራል፡፡ ነገር ግን ልዩነት ይኖራል ሲባል በሁሉም ነገሮች በግድ መለያየት አለብን ማለት አይደለም፡፡ ልዩነትን ተገድደን የምንቀበለውና ለማጥበብም ከልብ የምንጥርበት ሊሆን ይገባዋል እንጂ በ“ማን ምን ያመጣል?” የፈግጠው ፈግጪው ሁከተኛ መንፈስ አነሳሽነት በቤተ ሙከራ ተፀንሶ የሚወለድና የሚያድግ በጥባጭ “in vitro son” ሊሆን አይገባም፡፡ አንድ ሊያደርጉን የሚችሉ ነገሮች መኖር አለባቸው፤ ማወቅ ስለማንፈልግ ይሆናል እንጂ የምንጋራቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ለምሳሌ ተቃዋሚዎችንና ወያኔን አንድ ሊያደርጉ የሚችሉ ነገሮች አይኖሩም ብዬ በበኩሌ አላምንም፡፡ በዚህኛውም ሆነ በዚያኛው ጎራ እንደአለመታደል ሆኖ ሁሉንም ነገር የመቃወም ባህል ስላዳበርን እንጂ በምንስማማባቸው ነገሮች እየተስማማን በማንስማማባቸው ነገሮች ብቻ ብንነጋገር ኖሮ ትልቅ ሸክም ከትከሻችን በወረደልን ነበር፤ ግን አንዱ ስንጥቅ ሌላውን ሸለቆ እየፈጠረ ነገረ ሥራችን ሁሉ ባቢሎን ሆኖ ቀረ፡፡ ልዩነት ደግሞ በባሕርይው ቶሎ ካላጠበቡትና ከነጭርሱ ካላጠፉት እየተምቦረቀቀ የሚሄድ ክፉ ደዌ ነው፡፡ በአሁኑ ሁኔታችን በአንድ ጎራ ውስጥ አሉ በሚባሉ ወገኖች መካከል እንኳን የልዩነት ቀዳዳዎች ሲሰፉ እንጂ ሲጠቡ አይስተዋሉም፡፡ ይህም መረገም ነው፡፡

ከዚህ አኳያ ያ የበቀደሙ ጽሑፍ በተለይ የዘወትር ደምበኛው በሆንኩት አንድ ድረገፅ ላይ ሳይወጣ ሲቀር ደንግጫለሁ፡፡ በተደጋጋሚ ብጠይቅም እነአያ ሰው ጤፉ ፀጥታን መርጠዋል፡፡ የሕዝብ ነፃነት ተሟጋች ማለት እንግዲህ እንዲህ ነው፡፡ ውሸታም በሏቸው፤ እኔም ብያለሁ፡፡ የአንድን ዜጋህን ጥያቄና ብሶት ለመጋራትና ስሜቱን ለመረዳት፣ ተረድተህም ለማረጋጋት ካልሞከርክ፣ ከዚያም ባለፈ በትዕቢት ተወጥረህ ከተጓደድህበት ውሸታምና የይመስል ታጋይ ነህ – “ፑቲካ!”፡፡ አንድ ዜጋ ክቡር ነው፡፡ ትግላችንም ለዚያ ነው፡፡ እኛ ዘንድ የሌለን መከባበርና መደማመጥ እሌላ ቦታ መፈለግ ላም ባልዋለበት ኩበት ለመልቀም እንደመሞከር ነው፡፡

አንድ ወቅት በጣሊያን ሀገር ለውኃ በተቆፈረ የ36 ሜትር ጥልቀት ጉድጓድ ውስጥ አንድ ሕጻን ይገባና መንደርተኛውና ጠበብቱ ሁሉ እንዴት ሕጻኑን ማውጣት እንደሚቻል በጉድጓዱ ዙሪያ ከብበው ይጨነቃሉ፡፡ በዚህ መሀል ወሬውን በተባራሪ የሰማው የሀገሪቱ ርዕሰ ብሔር ይመጣና አብሮ እየተጨነቀና እያዘነ ከሕዝቡ ጋር ሙሾ ያወርድ ገባ፡፡ ሰው ማለት እንዲህ ነው፤ መሪ ማለትም፡፡ ዜጋቸውን እንደትቢያ የሚቆጥሩ ወያኔዎችን የምንታገለው ሌላ የአፈና ሥርዓት አምሮን ሣይሆን የመሰለንንና የምናምንበትን የኛን እውነት በነፃነት መግለጽ እንድንችል ነው፡፡ እርግጥ ነው – አንድ ሰው ወይም አንድ ቡድን የተጻፈው ነገር ትክክል አይደለም ብሎ ሲያምን በዚያው መድረክ በተመሣሣይ መሣሪያ – በብዕር – አጸፋውን በመስጠት የማስተባበልና የማስተማርም ግዴታ አለበት፡፡ ከዚያ ውጪ ወደ አፍ እላፊና እጅ እላፊ እንዲሁም ወደመኮራረፍ መሄድ ከሰውነት ደረጃና ክብር መውጣት ነው፡፡ ሰዎች ወደነዚህ ጅላጅል አማራጮች የሚዞሩት ትግስት በማጣታቸው ብቻ ሣይሆን የእውነት ስንቅ ስለሚያጥራቸው በካፈርኩ አይመልሰኝ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ አዎ፣ እውነት ስታጥረን ሀሰት ከተፍ ትልና የተጓደለውን ነገር በዛቻም፣ በስድብና በጡንቻም ታሟላልናለች፡፡

የኔን ወረቀት ቦጫጭቆ የጣለው ያ ድረ ገፅ ግን አሁንም ድረስ ግራ እንዳጋባኝ አለ፡፡ እንደሰው ድረገፅ ከፍቶ ማስተናገድ ከጀመሩ በኋላ ቀጫጭን ሰበብ እየፈለጉ ተናጋሪን ለማፈን መሞከር ሳቢውን ግረፈው እንዲሉ ነው፡፡ ያበጠው ይፈንዳ – ይህ ዓይነቱ አፈና ከወያኔ ያልተናነሰ ብልግና ነው፡፡ ያ ጽሐፍ በዚያ ድረገፅ የቅርጫት እራት (በኮምቡጠር ቋንቋ የ“Trash” ቀለብ) ሆኖ ይቀራል ብዬ በእውኔ ቀርቶ በህልሜም አላሰብኩትም፡፡ ከናካቴው ያዩትም አልመሰለኝም፤ አይተውት ከሆነና በምንም ምክንት ይን ከተውት ግን በርግጥም የሚዲያ ሥራን አያውቁም፡፡ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ችግር ቆሜያለሁ የሚል “የነፃነት ዐርበኛ” ያን የመሰለ ከመስከረም በሉት፣ ከየካቲትም በሉት(በተወሰነ ደረጃም ቢሆን)፤ ከግንቦትም በሉት ከሌላ ማናቸውም ንቅናቄ ምንም ያህል የጠበቀ ግንኑነት የሌለውን ማኅበራዊ ጉዳይ ገሸሽ ሲያደርገው “የሚሠሩትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” የሚለውን ክርስቶሳዊ ተማጽኖ ከማስታወስ ውጪ ሌላ ቃልም ሆነ አስተያየት የለኝም፡፡ የሚዲያ ሥራ ሆደሰፊነትን፣ ዕውቀትና ችሎታን፣ ሃቀኝነትን፣ አለማድላትን፣ አለማግለልን፣፣ ሙያዊ ትምህርትና ሥልጠናን፣ በጥቅም አለመደለልን … ይፈልጋል፤ ፈራጅና ዳኛው አንባቢ ወይም አድማጭና ተመልካች እንጂ እሱ የመረጠለትን ብቻ የሚያሣልፍ ከሆነ መጥፎ አሣላፊ ሆነ ማለት ነው፡፡ ጋዜጠኛ በሁለት የተራራቁ ጫፎች መሀል የተቀመጠ የሁለቱም ጫፎች የወል አገልጋይ እንጂ ከሁለቱ ወደ አንድኛው የሚሳብ ሊሆን አይገባም – ሰው ነውና አይሳብ አልልም፤ በሥራው ላይ እስካለ ግን አንዱን በመውደድ ሌላውን በመጥላት ሚዛኑን የሚስት ከሆነ የፓርቲ/የድርጅት ልሣን እንጂ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ሥነ ምግባር የሚፈቅደው አሠራር አልተከተለም – ኅሊናውንም አቆሸሸ፡፡ ከዚህ መሠራተዊ መርህ አኳያ ድረገፆቻችን ቢፈተሹ … ለነገሩ ማነው ወንዱ ለመፈተሸ የሚነሣ! ማንስ ሊሰማው፡፡ ለማንኛውም ማንም ደመ ሞቃት ካለበቂ ሙያዊ ዕውቀትና ግንዛቤ ከሜዳ እየተነሣ ጋዜጠኛ ልሁን ቢል ኢቲቪን ከሚያስታውሰን በስተቀር ሊታይና ሊጨበጥ የሚችል የረባ ሥራ አይሠራም፡፡ ዐርፎ እቤቱ ቢቀመጥ ወይም ሌላ ነገር ቢሠራ ነው የሚሻለው፡፡ ከልብ ነው ያዘንኩት፡፡ ሰው ደግሞ በወደደው ያዝናል፡፡ አለበለዚያማ ስንትና ስንት ሺህ ድረገፅ ሞልቶ የለም እንዴ? ደግሞ ለድረገፅ! የኮምፒውተር እናት በድባብ ትሂድ፡፡ እኔም እዚህ ሀገር ውስጥ ቀረቀር ውስጥ አጓጉሊት ተሰንቅሬ ባልገኝ ኖሮ አሥሩን ከፍቼ አራውጠው ነበር፡፡(ብዙ ጊዜ የሚያሣዝነኝ ነገር – ብዙ ነገሮች ወደኢትዮጵያ ሲገቡ ተፈጥሯቸውን ይለውጡና amorphous ይሆናሉ – ቅርጽ አልባ፡፡ ጥሎብን ፖለቲካችንም ሸፋፋ፣ ንግዳችንም ሸፋፋ፣ ዕድገታችንም ኳሻርኳራዊ ምች ያጠናገረው ግንጥል ጌጥ፣ የትምህርት ሥርዓቱ ሸፋፋ፣ መንግሥታዊ ተቋማችን ሸፋፋ፣ የግብርና የቀረጥ አተማመን ደንባችን ሸውራራ፣ መሪዎቻችን የአእምሮ መካኖች፣ አንዳችን ለአንዳችን ያለን አመለካከት ሸፋፋ፣… በአሁኑ ወቅት ምን ያልተንሻፈፈ ነገር አለን? በመጪው ዘመን ስንቱን ሸፋፋ አቃንተን እንደምንዘልቀው ፈጣሪ ይወቅ፡፡)

ወደጥንተ ነገራችን እንመለስ፡፡

ባጭር ባጭሩ ልንገራችሁ፡፡ ዘመናዊ ባርነት በኢትዮጵያ ነግሦኣል፡፡ እንዲህ ስላችሁ ባለፈው ጦማሬ እንደገለጸኩት ብዙዎቻችን የምንጠበስበትን የኑሮ ውጣ ውረድና የፖለቲካ እመቃ ማለቴ አይደለም፡፡ ከዚያም የከፋ የለዬለት ዘመናዊ ባርነት አለላችሁ፡፡(በነገራችን ላይ ባለፈው ጽሑፌ የአንድ ኪሎ ብርቱካን ዋጋ 22 ብር ገደማ ያልኳችሁ በጣም ተሳስቻለሁ – 45 ብር ገብቷል አሉ፤ ልብ አድርግ የአንድ ኪሎ ብርቱካን በችርቻሮ የመሸጫ ዋጋ 45 ብር ብቻ! ጉድ በል ጎንደር ማለት አሁን ነው፡፡)

ሚሚ ስባሃቱን የማያውቅ መቼም አይኖርም፡፡ የማታውቋት ካላችሁ – በቪኦኤ የአማርኛው ክፍል ትሠራ የነበረች፤ ከዚያ ተባርራ ይሁን በራሷ ፈቃድ ወጥታ ወደኢትዮጵያ የገባችና በርሷና በባሏ ስም የመነሻ ፊደላት “ዛሚ” ተብሎ በሚጠራ የኤፍኤም ሬዲዮ ጣቢያ በአብዛኛው ወያኔን እያገለገለች የምትገኝ “ጋዜጠኛ” ናት – አንዳንድ ማኅበራዊ ችግሮችን ማንሳቷንም አልክድም፤ ይህንን በጎ ሥራዋን በአወንታዊነት አደንቃለሁ፡፡ … አዜብ መስፍን የምትባለዋን ጉድ ደግሞ የማያውቅ ይኖራል ብዬ አልገምትም፡፡ እንደድንገት የማያውቅ ቢኖር አዜብ መስፍን ወይም አዜብ ጎላ ማለት የቀድሞውንና የዐፅመ-ዕድሜ ልክ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ጨምሮ የብዙዎች ሚስት እንደነበረችና እንደሆነች በብዛት የምትታማና – የአሁን ሁኔታዋን እንጃላት እንጂ – ወንዶችን ብቻ ሣይሆን ንግዱንና የንግዱን ማኅበረሰብ በሞላ እንደፈለገች የምታተረማምስ ሦስተኛዋ ዮዲት ጉዲት እንደሆነች የሚነገርላት ልዩ እስፊንክስ(Sphinx) ናት – ወደመጀመሪያዋ ዮዲት መሄድ ሳያስፈልገን ከሌላኛዋ መበለት ከገነት ዘውዴ ቀጥላ መሆኑ ነው ሦስተኝነቷ፤ ( እንዳለመታደል ሆኖብኝ አንዳንዴ ፈታ ብሎ መናገር ደስ ስለሚለኝ እንጂ ስለዚች ሴትዮ የግል ጠባይ እዚህ መናገሬ ስህተት መሆኑን ዐውቃለሁ፤ ሂሴን ውጫለሁ፡፡) እነዚህ ሁለቱ አዜብና ሚሚ የሚሰኙ ጉዶችና ሌሎች እነሱን የተከተሉ ጥቂት የማይባሉ ባሪያ ፈንጋዮች በሀገራችን የሚሠሩት ተዓምር ልዩ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ የዛሬ አሥራ ሦስት ዓመት ገደማ በአንድ ታዋቂ የግል ጋዜጣ አንድ መጣጥፍ ማውጣቴ ትዝ ይለኛል – ሰሚ ግን አልተገኘም፡፡ መጯጯኽ እንጂ መደማመጥ ብሎ ነገር ኢትዮጵያ ውስጥ ጭራሽ የለም፡፡

ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ የነሚሚና አዜብም ሆነ የሌሎቹ በሥራ አስቀጣሪነት ፈቃድ አውጥተው በሕዝብ የሚነግዱ ድርጅቶች ሠራተኞችን “ሥራ እናስቀጥራችኋለን” በሚል በየሙያ ዘርፉ ይመዘግባሉ፤ ይመለምላሉ፡፡ የተወሰነ የአጭር ጊዜ ሥልጠናም ሳይሰጡ አይቀሩም፡፡ በተለይ የጽዳትና የጥበቃ ሠራተኞችን፣ የጉልበት ሥራና መሰል አገልግሎት የሚሰጡ ሠራተኞችን የሚፈልጉ መሥሪያ ቤቶች ወደነዚህ ባሪያ ፈንጋዮች ዘንድ በመሄድ የሚፈልጉትን የሠራተኛ ዓይነት እንደፍላጎታቸው መርጠው ይወስዳሉ፡፡ ቀጣሪዎች፣ ደሞዝ ከፋዮች፣ አስጠንቃቂዎች፣ ከሥራ አሰናባቾች፣ … እነዚሁ አስቀጣሪ ድርጅቶች ናቸው፡፡ ሰዎቹን ወስዶ የሚያሠራቸው ድርጅት ግንኙነቱ ከ“ባሪያዎቹ” ጋር ሣይሆን ከአስቀጣዎቹ ድርጅቶች ጋር ነው፡፡ ይህ ዘመናዊ የባሪያ ፍንገላ አሠራር በሀገር ውስጥ ብቻ የተወሰነ አይደለም፡፡ መንግሥት የፈቀደላቸው የሚባሉ ወደውጪ ሀገራት በተለይም ወደዐረቡ ዓለም የቤትና የጉልበት ሠራተኞችን የሚልኩ አሉ፡፡ የሚያስከፍሉት ገንዘብ አንጀትን ይመዘምዛል አሉ፡፡ የነሱን የመጓጓዣና የደላላ ወጪ ለመክፈል የሚፈጀው ጊዜ የወላጅንና የተደጓሚ ቤተሰብን አንጀት በርሀብ ያነጥፋል፡፡ በዚያ ላይ አንዴ ከላኳቸው በኋላ ቢቀቀሉ ቢገነተሩ መብታቸውን ለማስከበር ዘወር ብለው አያዩዋቸውም ይባላል፡፡ አበሻ እንዲህ ሆዳምና ጨካኝ የሆንነው ግን ከመቼ ጀምሮ ይሆን እባካችሁ? የነሚሚ ጦስ ድንበር ዘለል ነው፡፡ ገንዘብ ባለበት ወያኔ አለ፡፡ ንግድ ባለበት – እዚህ በተጨባጭ እንደምናየው ሰውም ይሸጥ መሬትና ተንቀሣቃሽ ንብረትም ይሸጥ – ወያኔና የሙስና እናት የምትባለዋ አዜብ አይጠፉም፡፡ ይቺ የመርገም ፍሬ ሴትማ የጉልት ሴቶችን ሳይቀር በሽርክና አስገቡኝ ከማለት አትመለስም ይባላል – ፈጣሪን ምን ብንበድለው ይሆን ግን ለዚህ ለወሬ እንኳን ለማይመች መከራና ስቃይ የዳረገን? ይህችን ሴት ባሰብኩ ቁጥር አንዳርጋቸው ጽጌ(አንዱ) የተናገራት cringe የምትል ቃል ትዝ ትለኛለች፤ አዎ፣ ምን የመሰለ ድንቅ ታሪክ ያለን ሕዝብ ይቺን በመሰለች ሴት ስንታመስ በርግጥም መሸማቀቅ ሲያንሰን ነው፡፡ ለማንኛውም በነዚህ ሴቶችና ተባባሪዎቻቸው መሬት መሸከም የሚከብዳት ግዙፍ ግፍና በደል እየተፈጸመ ነው፡፡ ከፍ ሲል የጠቀስኩላችሁ የሀገር ውስጥ ባሪያ ፍንገላ የደመወዝና የጥቅማጥቅም ነገር ሲነሳ ነው ግፉ ቁልጭ ብሎ የሚታየን፡፡ በጥቂቱ እንየው፡-

እኔን የቀጠረኝ የግል ድርጅት ከነዚሁ የድሃን ደም መጣጮች ነው የጽዳትና የጥበቃ ሠራተኞቹን የተኮናተረው፡፡ እነዚህ ምሥኪን ሠራተኞች ደሞዛቸውን የሚያገኙት ከኛ ድርጅት ሣይሆን ከቀጠራቸው አስቀጣሪ ድርጅት ከነሚሚ ወይም ከነአዜብና መሰሎቻቸው ነው – አንዳች ሳይለፉ በድሃው ጉልበት የማይነጥፍ የነዳጅ ጉድጓድ የቆፈሩ ዘራፊዎች፡፡ የኔ መሥሪያ ቤት ለአንድ ጥበቃ ብር 1100(አንድ ሺህ አንድ መቶ ብር) ለቀጣሪ-አስቀጣሪው ድርጅት ይከፍላል፡፡ አስቀጣው ድርጅት ከዚህ ገንዘብ ውስጥ ግማሹን ለሥራ ማስኬጃ ይቀነድብለትና ግማሹን ብር 550 ለሠራተኛው በየወሩ ይከፍለዋል – በመረጃ የተደገፈ ወሬ ነው የምነግርህ፡፡ ይህ ሠራተኛ የኛ ድርጅት ቋሚ ቅጥር ቢሆን ኖሮ አንደኛ ደሞዙ ከዚህ አሁን ከሚከፈለው ሻል ሊል ይችል ነበር – የኛ ድርጅት ጭንቅላት የለውም እንጂ ቢኖረው ኖሮ ማለቴ ነው፡፡ ሁለተኛ የሕክምና ዋስትና ይኖረው ነበር፡፡ ሦስተኛ የጡረታ ዋስትና(Provident Fund) ይቆረጥለት ነበር፡፡ አራተኛ የሥራ ዋስትናው አሁን ካለበት ሁኔታ በጣም የተሻለ ይሆንለት ነበር(አሁን እንደ ዕቃ ነው፤መናገር፣ ማጉረምረም፣ መውቀስ፣ ምናምኒት አይችልም – ወዲያውኑ ይባረራል፡፡) እኛ ቢያንስ በግል ስንገናኝ የማጉረምረም መብታችን የተጠበቀ ነው፡፡ እነዚህ በወር 550 ብር የሚከፈላቸው የጥበቃና ጽዳት ሠራተኞች ባለፈው ጦማሬ የገለጽኩላችሁን የአዲስ አበባ የኑሮ ውድነት እንዴት ሊቋቋሙት እንደሚችሉ እንግዲህ አስቡት፡፡ የዱሮ ባሪያ ደረጃውን የጠበቀ አይሆን እንደሆነ እንጂ ቢያንስ በሕይወት ሊያኖረውና ሥራውን በአግባቡ እንዲሠራ ሊያደርገው የሚችል ምግብ ይሰጠው ነበር፡፡ የዘመናዊ ባርነት ሰለባዎች ግን የላባቸውን ውጤት የሚበላው ሌላ በመሆኑ ለትራንስፖርትም በማይበቃ ገንዘብ ጉልበታቸው ይበዘበዛል፤ ሥራ አላቸው እንዲባሉ ግን ውለው ይገባሉ፡፡ እነዚህ አስቀጣሪ ድርጅቶች በመያዶችና በዓለም አቀፍ ድርጅቶችም ያስቀጥራሉ፡፡ ከዚያም አካባቢ እንደሰማሁት ባሪያ ፈንጋዮቹ በብዙ ሺዎች ይቀበሉና ለሁለተኛ ዙር ተቀጣሪው ሠራተኛ የሚያቀምሱት በቡና ሥኒ ነው አሉ፡፡ ሰው ሌላ አማራጭ ስለሚያጣ በግዱ ወደነዚህ ድርጅቶች ይሄዳል፡፡ ወደ አሠሪዎቹ ድርጅቶች ሄዶ መቀጠር እንዳይችል እነዚህ የኔን ቀጣሪ ድርጅት መሰል ድርጅቶች ኃላፊነትን ይሸሻሉ፡፡ ከሠራተኛ ቁጥጥር፣ ከጥቅማጥቅም፣ ከሠራተኛና አሠሪ የክስ ውጣ ውረድና ከመሳሰለው የተገላገሉ እየመሰላቸው በእጅ አዙር የሰውን ጉልበት ይበዘብዛሉ፡፡ ግፍ በየዓይነቱ የሚናኝባት ብርቅዬ ሀገር አለችን፡፡

መፍትሔው ምን ይሁን ትላላችሁ? መፍትሔው እንደኔ የአስተሳሰብ ለውጥ ነው፡፡ የወያኔ ዓይነቱ ትውልድን አምካኝ የትምህርት ሥርዓት ሣይሆን ሥጋንና ነፍስን የሚያስታርቅ መንፈሣዊና ዓለማዊ ትምህርት ያስፈልገናል፡፡ በኢትዮጵያችን የሞራል ዕሤቶች ታጥበው ገድል ከገቡ በኋላ ይመስለኛል ይህ ዓይነቱ የጅብ ባሕርይ ወደ ሰዎች የተጋባው፡፡ እንጂ አምስት መቶ ብር ለውሻው የወር ባጀት እንደማይሆን የሚረዳ አንድ ሀብታም “ኢትዮጵያዊ” ዜጋ እንዴት አንድ መሰል ዜጋውን በዚህ ደሞዝ ያሠራል? ምን ዓይነት ደደብነት ነው? በተዘዋዋሪ ቀጥሮ የሚያሠራቸው ድርጅትስ ቢሆን ምናለበት ይህን ችግር ተገንዝቦ ራሱ በቀጥታ ቢቀጥራቸውና ያን አላግባብ የሚመዘበር ገንዘብ ለነሱ ቢያደርገው? ምን ዓይነት ሁልአቀፍ የሆነ የአስተሳሰብ ስንኩልነት ነው እየታዘብን የምንገኘው? አእምሮ ወዴት ገባ? ወዴት ሸፍቶ ይሆን? እዚች ላይ ትንሽ እንጸልይ መሰለኝ፡-“ አቤቱ የሰማዩ አባታችን እግዚአብሔር ሆይ፣ በሞራ የተሸፈነ ኅሊናችንን ግለጥልንና እውነቱን እንድናይ አድርገን! ለሰዎችም እንድናዝን የርህራሄና የመተሳሰብን መንፈስ በላያችን አሳድርልን፡፡ ለይቶልን ሳንጠፋ ጭል ጭል በምትለዋ እስትንፋሳችን ላይ ሞልቶ ከሚፈሰው የማያልቅ ቸርነትህ ላክልንና ወደየልቦናችን ተመልሰን እንድንተዛዘን፣ እንድንፈቃቀድም አድርገን፡፡ ጨርሰን ሳንጠፋብህ በመሀከላችን ገብተው የሚያበጣብጡንን የፍቅረ ንዋይና የአምልኮተ ንዋይን መንፈስ፣ የዘረኝነትና የሙስናን ደዌያት አስወግድልን፡፡ አሜን፡፡”

ችግርን ከማውራት የምገላገልበትን ጊዜ በጣም ናፍቄያለሁ፡፡ ሁልጊዜ ስለችግር ስለማወራ ራሴኑ ጭምር እንደችግር ማየት ከጀመርኩ ቆይቻለሁ፡፡ ከዚህ ቅኝት ለመውጣት ወደፊት ትልቅ ትግል ሳይጠብቀኝ አይቀርም፡፡

ወደ ሌላ ችግር፡፡ ሰሞኑን የወያኔው መንግሥት 37ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በዕጣ ማከፋፈሉ ይታወሳል፡፡ ዕጣ አወጣጡ ራሱ ችግር እንዳለበት ሰምቻለሁ፡፡ እመለስበታለሁ፡፡

ዕጣ ያልወጣላቸው ሰዎች “እንኳንስ ዕጣ አልደረሰኝ!” እያሉ የሚደሰቱበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ምክንያቱም አስቀድሞ የሚከፈለው ገንዘብ ከየት መጥቶ ይከፈል? ዕጣ የደረሳቸው አንዳንድ ጓደኞቼ “ምን ቅብጥ አድርጎኝ ነው የተመዘገብኩት”እያሉ ሲያማርሩ ታዝቤያለሁ፡፡ ምዝገባው የተካሄደው ቀደም ሲል ነው፡፡ ሰው ደግሞ ሲመዘገብ አንዳንዱ ለደራ ነው – ዕድሉን ለማየት፡፡ አንዳንዱ – እንዲያውም ብዙው ከመኖሪያ ቤት ችግሩ አንጻር ነው፡፡ አንዳንዱ ለትርፍ ነው – ቤት እያለው ግን ኮንዶምንየሙን ሸጦ ትርፍ ለማግኘት፡፡ አቤት የመጥፎ ጠባያችን አበዛዙ! ስንትና ስንት ሌላ አማራጭ እያለው ለዚች የአንድና የሁለት ክፍል ጎጆ ከድሃው ጋር ሙሉ ቀን ተሠልፎ የድሃውን ዕድል የሚያሰነካክል ሀብታም ታያለህ፡፡ በሚስቱም በልጁም በዘመዱም ስም ብዙ ቤት እያለው ለዚች ትንሽዬ ነገር የድሆችን ዕድል ሲያጨነግፍ የምታየው ገብጋባ ሰው አለ፡፡ ብዙ ችግር እኮ ነው ጓዙን ጠቅልሎ ወደሀገራችን የገባው፡፡ ለሰው ደግ መመኘትና “ይህ ለኔ በቂ ነው፤ ይህም የሌላቸው አሉና ለነሱ ይሁን” ብሎ ማሰብ ቀርቷል፡፡ እናላችሁ አዳሜ ዕድሏን ለመፈተንና “ከዚህ ወይ ከዚያ በማገኘው ገንዘብ አሟልቼ ቅድሚያ ክፍያውን እከፍላለሁ፣ ከዚያም እኔ በአነስተኛ ገንዘብ እከራይና ቤቱን በትልቅ ዋጋ አከራይቼ ወይ ሸጬ በማገኘው ትርፍ ዕዳየን በቶሎ አጠናቅቃለሁ” ብላ አስባ ስታበቃ አሁን ዕጣው ሲወጣላት ጊዜ ምኑን ከምን ታ’ርገው? ለምሳሌ በምዝገባው ወቅት 60ሺህ ብር ገደማ ተብሎ የተነገረው የባለ ሁለት መኝታ ቤት ኮንዶምንየም የቅድሚያ ክፍያ አሁን በወቅቱ የገንዘብ ምንዛሬ ተሻሽሎ ከ80ሺህ ብር በላይ ሆኗል፡፡ አንዱ ጓደኛየ የዚሁ ቤት ዕጣ ደርሶት ዕጣው ከወጣበት ዕለት ጀምሮ የሌት እንቅልፉንና የቀን ሰላሙን አጥቷል፡፡ የርሱ ደሞዝ ከዕለታዊ መጠነኛ ኑሮ አያልፍም፡፡ በዕቁብም ሆነ ወደፊት የሚከፈል ተብሎ በብድር መልክ ከሰው ማግኘት የሚታሰብ አይደለም – ከመነሻው ድሃን አምኖ የሚያበድረውም የለም፡፡ ብድርና ቁጠባ ቢል ያጠራቀመው በጣም ጥቂት ነው፡፡ ፒኤፍ ቢጠይቅ እሺ አልተባለም – ቢፈቀድለት እንኳን አይሞላለትም፡፡ ሥራውን ለቅቆ ፒኤፉን እንዳይወስድ በዛሬ ጊዜ በመከራ የሚገኝና በዘመድ አዝማድ በተቆላለፈ ማኅበረሰብ ውስጥ ሌላ ሥራ መፈለጉ መድሓኒት የሌለው ትልቅ ራስ ምታት ነው፡፡ እናም እንዲሁ እየዋተተ አለ፡፡ በዚህ ሁኔታ የሚቸገሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ ይህ አጋጣሚ ደስታ ሀዘንን ሲወልድ ያየሁበት ልዩ አጋጣሚ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ይህን የኮንዶምንየም ቅድሚያ ክፍያ በሴከንድ ውስጥ የሚከፍሉ ግን ባለአነስተኛ ደሞዝተኞች አሉ፡፡ እነዚህም የሙስናው ሞተር አሽከርካሪዎችና ልየ ልየ የጎን ገቢ ያላቸው ናቸው፡፡ ሙስና ካለ እንኳንስ ኮንዶምኒየም ኦሮጵላንም ይገዛል፡፡ ይብላኝ ዙሪያ ገባው ለጨለመበት ተራው የመንግሥትና የግል ድርጅቶች ሠራተኛ! ይብላኝ በረንዳዎችን ሙጥኝ ብሎ ለሚገኘው በመቶ ሺዎች ለሚገመተው ዜጋ፡፡ ስለወቅቱ የሥራ አያያዝ ሁኔታ ግን ትንሽ ላውራችሁ፡፡

በዛሬ ጊዜ ይገርማችኋል ወርቅ የሆነ የሥራ ችሎታና ወርቅ የሆነ ጠባይ ቢኖርህ ሰው የሚቀጥርህ ዘርህን ጠይቆ ነው፡፡ የሀገራችን ሠራተኛ ያሣዝናችኋል፡፡ በየጠላና አረቂ ቤቱ ስዘዋወር የምሰማው የዘረኝነት መዘዝ የፈጠረው ብልሹ አሠራር ዕበድ ዕበድ ነው የሚለኝ፡፡ ምን የመሰለ የግምበኝነትና የአናፂነት ሙያ እያለው ትግሬ ወይም ኦሮሞ ባለመሆኑ ብቻ የሚቀጥረው አጥቶ ሲንቀዋለልና በየቁንድፍት ቤቱ ጉበቱን ሲያቃጥል የሚውለውንና የሚያመሸውን ዜጋ በቤቱ ይቁጠረው ብቻ የምንተወው ሣይሆን እኔም ያቅሜን ተዘዋውሬ ተመልክቻለሁና እስክሞት የማይረሳኝ ዕድሉ ከገጠመኝም ምሥክርነቴን በኃያሉ አምላክ ፊት ሣይቀር የምሰጥለት የሀገራችን የወቅቱ ነቀርሣ ነው፡፡ ከዘበኝነት አቅም ዘርህና ጎጥህ ተቆጥሮና ማንነትህ ተጠንቶ ነው የምትቀጠረው – በር እየከፈተ መኪናን ማስወጣትና ማስገባትም ከቁም ነገር ተጥፎ እንዲህ ያለ መድሎ ይታያል፡፡

በዕጣው አወጣጥ ችግሮች እንደነበሩበትም ይነገራል፡፡ ወያኔ ለማስመሰል ድራማው በዕጣው ቤት ይደርሳቸዋል ተብለው ከማይጠበቁ ዜጎች ከዚህም ከዚያም ለአንዳንዶች ጣል ጣል አደረገ እንጂ የአንበሳ ድርሻውን ለራሱ ካድሬዎችና ለሚፈልጋቸው ወገኖች በዕጣ አስመስሎ እንደሸለማቸው በስፋት ይወራል፡፡ ለምሳሌ በአንድ መሥሪያ ቤት ለብዙ የሥራ ሂደት ባለቤቶችና የፖለቲካ ሠራተኞች እንደደረሰና ያን የመሰለ አጋጣሚ እንዴት በዕጣ ሊወጣ እንደቻለ መነጋገሪያ እንደሆነ ከቅርብ ሰው ተረድቻለሁ፡፡ ለነገሩ በህዳሴው ግድብ ሥራ ማስጀመሪያ የመጀመሪያዋ ዕለት እንደተወለደና ስሙም ህዳሴ ለተባለ ሕጻን የህዳሴው የስልክ ሎተሪ ዕጣ የመኪና ሽልማት እንደደረሰ በሚነገርባት ሀገር፣ አንዲት የ14 ዓመት ታዳጊ ወጣት በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቷ ባሳየችው የበጎ አድራጎት ሥራ የተመሰጡት ትምህርት ቤቷና ሌላ ድርጅት በጋራ ሆነው የኢትዮጵያን ዓመታዊ አጠቃላይ በጀት ሊሆን የሚዳዳው የ20 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት እንደተቀበለችና ያንንም ገንዘብ – ድምቡሎ ሣታስቀር(እንዴት ያለ ቱጃር ቤተሰብ ነው ያላት ጃል!) ለትምህርት ቤት ግምባታ ልታውለው ለመንግሥት እንዳበረከተች በሚነገርባት የወያኔ ኢትዮጵያ ውስጥ ይህ ዕጣ ሸር የለበትም ብሎ መቀበል ከየዋህነትም የዘለለ ሞኝነት ነው፡፡

በመጨረሻም አስቀድሜ እንደጠቆምኩት ትዝናኑበት ዘንድ አንድ ወንድም ከቦስተን ማሳሹተስ የላከልኝን ኢሜይል እንዳለ በኮፒ/ፔስት ከሥር አስቀምጣለሁ፡፡ “ያልተነካ ግልግል ያውቃል” ይባላል፡፡ እኔ በመምህር የሚታረም የፈጠራ ድርሰት የጻፍኩ ይመስል ስለ አጻጻፍ ሥልቴ አይረቤነት ያወራል፡፡ ችግራችንን ዘረዘርኩ እንጂ ሥነ ጽሑፍ አልጻፍኩም፡፡ ችግርን ለመናገር ደግሞ አንድ ሰው በልምድም ይሁን በትምህርት የሚያውቀው (አነስተኛም ቢሆን) የንግግርና የጽሑፍ ችሎታ በቂው ነው – መራቀቅና ተቺየ እንደሚለው coherence, cohesive device ቅብጥርስ እንዲያውቅ አይጠበቅበትም፡፡

Comment

 

The post ዘመናዊ ባሪያ ፍንገላ በኢትዮጵያ (ነፃነት ዘለቀ – ከአዲስ አበባ) appeared first on Zehabesha Amharic.

ማሞ ሌላ ፎቶግራፉ ሌላ –የፍራንክፈርቱ የኦህዴድ ስብሰባ

0
0

Frankfurt ethiopiaበልጅግ ዓሊ

ከጥቂት ዓመታት በፊት ጀርመን ፍራንክፈርት ማርዮት ሆቴል ውስጥ “ኢንቬስተሮችን“ ለመሳብ በሚል ፈሊጥ አባዱላ ገመዳ በተገኘበት የወያኔ አባላትና ደጋፊዎች ስብሰባም ተጠርቶ ነበር። በዕለቱ

ተቃዋሚዎች ከደጅ ተኮልኩለው ወያኔን በመቃወም ላይ ነበሩ። በሁለት ስለት ቢላዋ መብላት የዘመኑ ብልጠት በመሆኑ፤ የቤት መስሪያ ቦታ መደለያ ለማግኘት የሚቋምጡ ሁሉ በዚህ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ነበር። በተለይ የወያኔ ደጋፊ የሆኑ “የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ኢንቬስተሮች“ አለያም በዘመኑ አጠራር የልማት ባለሃብት ተብዬዎች ማንነታቸው በሰልፈኞቹ እንዳይለይ በመፍራት ማንነታቸውን በመነጽርና ኮፍያ ውስጥ በመደበቅ ወደ አዳራሹ ይገቡ ነበር። በሌላ ስልት ደግሞ ከተቃዋሚዎች መሃል አንዳንዶች ገብተው ስብሰባውን እንዲካፈሉና የስብሰባውን ይዘትና ጭብጥ ተረድተው እንዲወጡ ተደርጎ ነበር። ቀደም ሲል በስንት ጣር በመነጽርና በኮፍያ ታግዞና እራሱን ደብቆ የገባው “ኢንቬስተር“ ተሽቀዳድሞ ወደ ሽንት ቤት በመግባት ጣጣ እንደሌለበት ሰው ኮፍያውንና መነጽሩን አውልቆ፣ አለባበሱን አስተካክሎ ወደ ስብሰባው አዳራሽ ብቅ ሲል ከውስጥ ቀደም ሲል ሆን ተብሎ ለማጥናት የገባው ተቃዋሚ ይጠብቀዋል። እንደገና ሌላ መደናገጥ ይፈጠራል። ግማሹ መግቢያ ያጣል ፣ ግማሹ እንዳላየ አይቶ ለማለፍ ይሞክራል፣ አንዳንዱ ደግሞ እንደምንም እራሱን አረጋግቶ የማስመሰል ጨዋታውን ይገፋበታል።

More….

The post ማሞ ሌላ ፎቶግራፉ ሌላ – የፍራንክፈርቱ የኦህዴድ ስብሰባ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢትዮጵያዊቷ የISIS ሙሽራ እና “ጽንፈኛ” ሆነው የተገኙት አባቷ

0
0

kasahun
ከካሳሁን ይልማ(የኢሳት ጋዜጠኛ)
ይህ ጽሁፍ የተገኘው ከርሱ ፌስቡክ ገጽ ነው

አስደንጋጭ ዜና ነው። ራሱን የእስልምና ግዛት ISIS ብሎ የሚጠራው አክራሪ እና ጭራቂዊ ቡድንን ለመቀላቀል ከሁለት ጓደኞቿ ጋ ከለንደን ወደ ሶሪያ የሄደችው የ15 ዓመቷ አሚራ አባት የሆኑት አቶ አባስ ሁሴን Innocence of Muslims የሚለው ፊልም እስልምና እምነትን አዋርዷል በማለት በለንደን አሜሪካ ኤምባሲ ፊት-ለ-ፊት በተደረገው ሰልፍ ላይ አሜሪካ ትቃጠል፣ ሙስሊም ክሩሴድን ያጠፋል አሜሪካንና እንግሊዝን ጨምሮ…. የሚሉ መፈክሮች ጀርባ በስሜት መፈክር ሲያስተጋቡ የሚታዩበት ቪዲዮ ይፋ ሆኗል።

መፈክር ብቻ ሳይሆን የአሜሪካንና እስራኤል ባንዲራ ሲቃጠል አቶ አባስ አጃቢ ናቸው። ልጃቸው ወደ ሶርያ ለመግባት በቱርክ በኩል ስታቋርጥ በካሜራ እይታ ውስጥ ከገባችና ሁኔታው በእንግሊዝ መንግስት በገሊ ከተነገረ በኋላ አቶ አባስ የእንግሊዝን ፖሊስ ተጠያቂ ማድረጋቸው ይታወሳል። በወቅቱ በብሪታኒያ ፖሊስ ማዕከል ስኮትላንድ ያርድ ቃለምልልስ ሲሰጡ ልጃቸው ስለአክራሪነት ፈጽሞ የምታውቅበት መንገድ ይፈጠራል ብለው እንደማያምኑ ሳግ እየተናነቃቸው ሲናገሩ ሰምተናል።

ነገር ግን አሁን ቀስቱ ወድሳቸው ዞሯል። ከ3 ዓመታት (2012) በፊት የዛሬን ጦስ ሳያስቡት እንግሊዝን ባስበረገገው የጽንፈኞች ሰልፍ ላይ ተዋናይ መሆናቸው በቀላሉ የማይታይ፣ ለልጃቸው የISIS ነፍሰ ገዳይ ለመሞሸር ድንበር ማቋረጧ በቀጥታ ተጠያቂ መሆናቸው አይቀሬ ነው። አሜሪካንም ሆነች እንግሊዝ ጉዳዩን በቀላሉ አያዩትም። ለዚህ ምክንያቴ አቶ አባስ:–

1. የአሜሪካኑን 911 እና የእንግሊዙን 7 July 2005 የሽብርተኞች ጥቃትን በአደባባይ የደገፈው ብሪታኒያዊው አካራሪ፣ አክቲቪስትና የሙስሊም ማህበረሰብ ጠበቃዎች ሊቀመንበር አንጀም ቾዳሪ የመራው ሰልፍ ላይ መገኘታቸው

2. በዛ ሰልፍ ላይ ከታደሙት መካከል Michael Adebowale የተባለ ወጣት ከዚያ የጽንፈኞች ሰልፍ አንድ ዓመት በኋላ የብሪታኒያን ወታደር Lee Rigbyን በደቡብ ምሥራቅ ለንደን በጠራራ ፀሐይ በመኪና ገጭቶ በስለት ወጋግቶ የገደለ መሆኑ ልጃቸውን ከማጣታቸው ጋር ተደማምሮ የአቶ አባስን ቀጣይ ሕይወት መሪር ያደርገዋል። ሆኖም ሰው የዘራውን ማጨዱ አይቀርም ቢባልም በልጃቸው ማንነት ላይ የነበራቸውን ሚና እርግጠኛ ሆኖ መናገር አዳጋች ነው።

ሆኔታው ግን ለጅምላ ፈራጆች ትልቅ ሲሳይ እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ። የኢትዮጵያ ሙስሊሞች እንቅስቃሴን በጎሪጥ ለሚያዩ ሰዎች፣ ህወሓት የሚሰራው ፕሮፓጋንዳ ለኀይማኖታቸው፣ ለብሔራቸው… በሚመች መልኩ በትሪ ጠረጴዛቸው ላይ ቁጭ ሲቀርብ ተስገብግበው ለሚሻሙ ሰዎች ለቁንጽል መረጃቸውና ድምዳሜያቸው ግዙፍ ርዕስ አግኝተዋል።

ድምጻችን ይሰማ በዚህ ውዥንብር ሳይደናገር ላለፉት 3 ዓመታት ያሳየንን ሰላማዊ እና ስልጡን ተቃውሞ እንደሚቀጥል ቅንጣት ታህል ጥርጥር የለኝም።

The post ኢትዮጵያዊቷ የISIS ሙሽራ እና “ጽንፈኛ” ሆነው የተገኙት አባቷ appeared first on Zehabesha Amharic.


የሰማያዊ ታርቲ የስብሰባ ጥሪ

0
0

DCከአምባገነን አገዛዝ ወደ ፍት ሃዊ ስርአት ለመቀየር ባገራችን እየተካሄደ የሚገኘዉን እረጂም አና እልህ አስቆራጭ (ላንዳዶችተስፋ አስቆራጭ) ትግል ወደፊት ለማራመድ የሚያስፈልገውን መስዋትነት ለመክፈል ዝግጁ ሆነው በቆራጥነት ከሚታገሉሃይሎች ዉስጥ የሰማያዊ ታርቲ አንዱና ግንባር ቀደም ፓርቲ ነው። የዚህ ፓርቲ የሰላማዊ ትግል ስልት በኢትዮጵያ ተጨባጭሁኔታ አኳያ ሲታይ ዉጤት ሊያስገኝ የሚችል አካሄድ ነወይ? የሰማያዊ ፓርቲ በአገዝዙ እንደሌሎች ፓርትቲዎች እንዳይኮላሽእራሱን የሚጠብቅበት ስልት አለውን? በስርአቱ የይስሙላ ምርጫ በመሳተፍ ፓርቲው ለኢትዮጵያ ህዝብ ሊያስገኝ ያቀደውፋይዳ ምንድን ነው?

እነዚህንን እና ለሎችንም እጠያያቂ ጉዳዮችን ከኢትዮጵያዊያን ጋር ለመወያየት እንዲሁም ፓርቲዉ ለሚያደርገው ጥረት እገዛለመጠየቅ የታርቲው የወቅቱ ሊቀመንበር አቶ ይልቃል ገትነት በሰሜን አሜሪካ ጉብኝት ለማድረግ ሰሞኑን ይመጣሉ።

የዚህ ጉብኝት የመጀመሪያ ፕሮግራም በዋሺንግቶን ዲሲ በመጪው ቅዳሜ አፕሪል 4 ቀን ከቀኑ በ 2 ሰአት አርሊንግቶንቨርጂኒያ በሚገኘው ሸራቶን ፔንታገን ሲቲ ሆቴል ይካሄዳል። ሁለተኛዉ ፕሮግራም በቦስተን ከተማ እሁድ ኤፕሪል 5 ቀን ከቀኑብ 3 ሰእት በ 203 ሰመርቪል አቬኑ ሰመርቪል ማሳቹሴት ይካሄዳል

ይህን ፕሮግራም በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት የአንድነት እና የሰማያዊ የሰሜን አሜሪካ የድጋፍ አሰባሳቢ ድርጅቶች ሁሉምኢትዮጵያዊያን በቦታው ተገኝተው የዚህ ዉይይት ተካፋ እንዲሆኑና ድጋፋቸዉን እንዲያሳዩ ባክብሮት ጥሪ ያቀርባሉ

ለበለጠ መረጃ

ኢሜል:   info@semayawiusa.orgBoston

በስልክ:  (202) 556-3078

ድረገጽ:  www.semayawiusa.org

The post የሰማያዊ ታርቲ የስብሰባ ጥሪ appeared first on Zehabesha Amharic.

የዘውዲቱ ሆስፒታል ሊፍት ሰው ገደለ

0
0

(መንግሥቱ አበበ)

የዛሬ ሳምንት ከሰዓት በኋላ ነው፡፡ የ72 ዓመቱ አዛውንት አቶ ካሣሁን አበበ ታምማ ዘውዲቱ ሆስፒታል የተኛች እህታቸውን ለመጠየቅ ሄዱ፡፡ ሆስፒታል ደርሰው እህታቸው ወደተኙበት ክፍል ለመሄድ የሊፍቱን መጥሪያ ሲጫኑት ተከፈተ፡፡

liftሊፍቱ ተበላሽቶ ስለነበር ሰው መጫኛው ወለል አልነበረም፡፡ አቶ ካሳሁን ወለሉ ያለ መስሏቸው ዘው ብለው ሲገቡ ጉድጓድ ውስጥ እንደገቡ ልጃቸው ፍቅርተ ካሳሁን ተናግራለች፡፡

አቶ ካሳሁን “እርዱኝ እርዱኝ” እያሉ ሲጣሩ አንድ የጽዳት ሠራተኛ ሰምታ ሰው በመጥራት ተረባርበው ካወጧቸው በኋላ ወደ ድንገተኛ ክፍል እንደወሰዷቸው የገለፀችው ፍቅርተ፤ ወደ 10 ሰዓት ገደማ ቤተሰብ ተጠርቶ ሲደርስ አቶ ካሳሁን በፅኑ ይተነፍሱ እንደነበርና ጣቶቻቸው ከመጋጋጣቸው በስተቀር የሚፈስ ደም እንዳልነበረ ጠቁማለች። ልብሳቸው በተቃጠለ ዘይት ተለውሶ እንደነበር ጠቅሳ ትንሽ ቆይቶ ሕይወታቸው እንዳለፈ ፍቅርተ ገልጻለች፡፡ አደጋው ስለተከሰተበት ሁኔታ ለማወቅ ዘውዲቱ ሆስፒታል ብንሄድም የሆስፒታሉ አስተዳዳሪ ዕረፍት ላይ ስለሆኑ ልናገኛቸው አልቻልንም። እሳቸው የወከሏቸው ሜዲካል ዳይሬክተር “አሁን ስብሰባ ላይ ነኝ፡፡ ስለጉዳዩ ድንገተኛ ክፍል ጠይቁ። ለእኔም የነገሩኝ እነሱ ናቸው” ብለውናል። ድንገተኛ ክፍል ስንጠይቅ በዕለቱ ተረኛ የነበሩትን ዶክተሮች አነጋግሩ የተባልን ሲሆን ተረኛ ዶክተሮቹ በበኩላቸው፤ ኦፕሬሽን እያደረግን ስለሆነ እስክንጨርስ ጠብቁ አሉን። ሆኖም ማተሚያ ቤት የመግቢያ ሰዓታችን በመድረሱ ምላሻቸውን ለማካተት አልቻልንም፡፡
አቶ ካሳሁን የ3 ወንዶችና የ5 ሴቶች አባት ነበሩ።

Source: Addis Admass Newspaper

The post የዘውዲቱ ሆስፒታል ሊፍት ሰው ገደለ appeared first on Zehabesha Amharic.

(የሳኡዲ ጉዳይ) “በሁቲ አማጽያን ላይ የተጀመረው ጥቃት አያቆምም!”–የሳውዲው ንጉስ ሰልማን ቢን አብድልአዚዝ

0
0

saudi 1

saudi

የመረጃ ግብአት ( Update )

“በሁቲ አማጽያን ላይ የተጀመረው ጥቃት አያቆምም! ”
የሳውዲው ንጉስ ሰልማን ቢን አብድልአዚዝ
==============================

* የአረብ ሊግ ሀገራት መራሄ መንግስታት በየመን ጉዳይ ለመመከር ግብጽ ሻርማ ሸክ ተሰብስበዋል ።

* የዘመቻው መሪ ሀገር የሳውዲ ንጉስ ሰልማን ቢን አብድልአዚዝ ” የመን እስክትረጋጋ በሁቲ አማጽያን ላይ የተጀመረው ጥቃት አያቆምም! ” ሲሉ በመክፈቻ ንግግራቸው አስታውቀዋል ።

* ከሳውዲው ንጉስ ሰልማን በተጨማሪ የየመን ተገፊ መሪ አብድረቡ መንሱር አለሃዲና የተለያዩ አረብ ሀገራት መሪዎች ንግግር በማድረግ ላይ ናቸው !

*** **** ***
“ዘመቻ ማዕበል ” የ3ኛው ቀን አበይት ክንውኖች …
==============================
*በሳውዲ የተመራው የህብረት ጦር በሁቱ አማጽያን እጅ በሰንአ እና በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል የሚገኘውን የብላስቲክ ሚሳየል ክምችት ballistic missile stockpile ማውደሙን አል አረቢያ ዘግቦታል

* ከየመን ሰንአ የህብረቱ የአየር ኃይል ጦር የደቡብ ከተማዋ በዳሊያ ባደረገው ወታደራዊ ይዞታዎች ኢላማ ያደረገ ድብደባ የሁቲ አማጽያን ጸረ አውሮፕላን በመተኮስ መልስ መስጠታቸውም ተጠቁሟል

* በሳውዲ ባህር ኃይል ሁለት የጦር መርከቦችና ኮማንዶዎችና አየር ኃይልና በልዩ ኮማንዶዎች በታገዘ ዘመቻ 86 የሳውዲ እና የምዕራባውያን ሀገር ዲፕሎማቶች ከወደብ ከተማዋ ከየመን ሁለተኛ ከተማ ከኤደን በተሳካ ዘመቻ መውጣታቸው ተጠቁሟል

* ዛሬ ማለዳ ሰንአ ውስጥ የሚገኙ የተባበሩት መንግስታት ሰራተኞችን ከሰንአ ለማስዎጣት የሳውዲው መከላከያ ሚኒስትር ሶስት አውሮፕላን መላካቸው ተዘግቧል ። የመንግስታቱ ድርጅት ሰራተኞቹን ለማሰረዎጣት ነጻ የአየር ክልል እንዲሰጥና ከሰንአ ወደ ኢትዮጵያ ለሚደረገው ማሸጋገር ትብብርን ከሁቲ አማጽያን ያቀረበው 140 ሰራተኞች እንዳይንቀሳቀሱ ጋሬጣ ባይጠፋኝ ጥያቄው ተቀባይነት ማግኘቱ ተነግሯል

* በአሜሪካ የሳውዲ አምባሳደር አድል አል ጃብሪ ኢራንና ሂዝቦላህ የሁቲ አማጽያንን ከጀርባ ሆነው እንደሚረዷቸው ከ CNN ጋር ባደረጉት ውይይት አስታውቀዋል

( ከዘመቻው ጋር በተያያዘ ፣ ጅዳ ውስጥ በትልቁ የአየር ማረፊያ ፕሮጀክቶች በህጋዊ መንገድ ይሰሩ ከነበሩት የመናውያን ጋር ኢትዮጵያውያንም “ለደህንነት” በተባለ ምክንያት ወደ አየር ማረፊያው ስራ ፕሮጀክት እንዳይገቡ መከልከላቸውን መረጃ ደርሶኛል )

እስኪ ቸር ያሰማን !

ነቢዩ ሲራክ
መጋቢት 19 2007 ዓም

The post (የሳኡዲ ጉዳይ) “በሁቲ አማጽያን ላይ የተጀመረው ጥቃት አያቆምም!” – የሳውዲው ንጉስ ሰልማን ቢን አብድልአዚዝ appeared first on Zehabesha Amharic.

ከ40 በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን በየመን መታፈናቸው ተገለጸ

0
0

yemen_10
በ ሬድዮ ዳንዲ ሃቃ
ቅዳሜ መጋቢት 19 /2007
ከ የመን ዋና ከተማ በሰነዐ ከሚገኘው መርከዛ ታዕዊን እና መርከዛ ሸርቂያ በ90 የሚገመቱ የዲን ትመህርት የሚከታተሉ ተማሪዎች የታፈኑ ስሆን እስከ አሁን የት እንደደረሱ አለመታወቁ ምንጮቻችን ገለጹ።
አፈናዉ ባለፈዉ ሴኞ 14 ተማርዎችን ከ ሁሌት መስጂዶች በማፈን የተጀመረ መሆኑን ምንጮቻችን ገለጸዋል።
ትላንት ጁመዓ ከሌሊቱ 8:00 ሰዓት 80 የሚሆኑ ተማሪዎች የታፈኑ ሲሆን ባጠቃላይ ወደ 94 ተማሪዎች ታፍነዉ መድረሻቸዉ አለመታወቁ ተገልፆዋል።
አነዚህ ተማሪዎች ለዲን ትምህርት ከሀገራቸዉ የተሰደዱ ሲሆን በብዛት ሐፍዘል ቁርአን ሲሆኑ ከመካከላቸዉ ሃዲስን የሀፈዙ ተማሪዎች መኖራቸዉን ለማወቅ ተችሏል። ተማሪዎቹ ሻርቄይን፣
ከፈትህ እና ሰዋን አከባቢ ከሚገኙ ሱኒ መስጂዶች የታፈኑ መሆኑን ምንጮቻችን አክሌው ገልጸዋል።
በተያያዘ ዜና በየመን በሸሪካ የሚሠሩ ወንድሞች ከሥራ ገበታቸዉ እየተባረሩ መሆኑ ተገልጿል።

The post ከ40 በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን በየመን መታፈናቸው ተገለጸ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኮሜዲያን ዳንኤል ቁንጮ አረፈ

0
0

daniel kuncho
(ዘሐበሻ) ተወዳጁ ኮሜዲያን ዳንኤል ቁንጮ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። በ አንድ ወቅት ስመ ገናና የነበረውና በ ኤግዚቢሽን ማዕከል በሚደረጉ ዝግጅቶች እና በቲቪ ፕሮግራሞች ላይ ኣጫጭር ጭውውቶችን ያቀርብ የነበረው ዳንኤል ቁንጮ ራሱን ወደ ዲጄነት ቀይሮም ፒያሳ ኣካባቢ በሚገኘው በኣካል ጸ ክለብ ውስጥ ለረዥም ዓመታት ኣገልግሉኣል።

ለዘሐበሻ ከኣዲስ ኣበባ የደረሱ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኮሜዲያኑ ታሞ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ነበር። ዛሬ በተክለሀይማኖት ሁስፒታል ህክምና ሲከታተል ሕይወቱ ያረፈው ዳን ኤል ቁንጮ የቀብር ስነስር ዓቱ ነገ ይፈጸማል ተብሎ ይጠበቃል።

The post ኮሜዲያን ዳንኤል ቁንጮ አረፈ appeared first on Zehabesha Amharic.

ፖለቲካ፣ ሐይማኖት፣ ዘር፣ በሰው ልቦና ውስጥ።

0
0

Ketemaፖለቲካ እና ፖለቲከኞችን ስንመለከት ባላደጉ አገሮች ለፖለቲካ ፍጆታቸው ሐይማኖትን እና ዘርን መጠቀሚያ ያደርጋሉ። የወያኔ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ማሳያው መንገዱ  ሐይማኖትና ዘርን ለርካሽ ስራው ወደ ሜዳው ያስገባቸዋል። እንደዚህ አይነቱ የፖለቲካ አካሄድ ከአጥፍቶ ጠፊ ቡድን ተለይቶ አይታይም። ሰው የተባለው ክቡር ፍጥረትን በሃይልና በማይፈልገው መንገድ በግድ  ፖለቲካዊ እውቀት ሳይኖራቸው ወደ ሜዳው ማስገባት የወያኔ ስልት ነው። የቀድሞ የወያኔ መሪ የነበሩት እንዲ ብለው ነበረ << ምርጥ ኢሕአዴግ ሁኑ ካልሆናችሁ በናንተ ላይ ሌላ ምርጥ ኢሕአዴግ እሾማለው>> ብለው እንደተናገሩት የሜዳ ውስጥ ጨዋታ ይሄ ነው። ወይ መሆን …አልያም ባንተ ላይ ሌላ መሾም። የትኛውም ሐይማኖት ተከታይ ሁን የትኛውም ዘር ሁን ወደ ሜዳው እንድትገባ ይደረጋል ከምርጥ ውስጥ የሆነ በሜዳው ይቆያል ከምርጥ ውስጥ ያልሆነ ደግሞ ይባረራል።

በስፖርቱ አለም ወደ ሜዳው የሚገቡት ሰውነታቸው  የዳበረ  እና በቂ ችሎታ ያላቸው ናቸው። በተለያየ ግዜ የተለያየ ግጥሚያ ካደረጉ በኋላ በልጦ የሰራ እና በቂ ችሎታ ያለው አሸንፎ ደጋፊውን አስጨብጭቦ የተዘጋጀለትን ዋንጫ እና የተለያዩ ሽልማቶችን ይወስዳል። ባደጉት አገሮች ልክ እንደ ስፖርቱ  ተመሳሳይ ነው። ጠንክሮ የሰራ እና ጥሩ የፖለቲካ ብቃት ያለው አሸንፎ የበላይነትን ያገኛል። የኛ አገር ግን እንደዚህ አይደለም። የአገራችን ፖለቲካ ሐይማኖትና ዘርን ወደ ሜዳው በጥቅም ተብትቦ እና  አስገድዶ  አስገብቷል። ገዢ  የተባለው አካል የራሱ ሜዳ ውስጥ ተገዢ የተባሉ ቡድኖችን ሁሉ በግድም ወይም በማግባባት አልያም በጥቅም እንዲገቡ ተደርጓል። ወደሜዳው የገቡት የፖለቲካ እውቀት፣ የሐይማኖት እውቀት፣ ስለዘር እውቀት የሌላቸውን ባልዳበረ  ችሎታ  ወያኔ ወዳዘጋጀው ሜዳ ገብተው መገኘቱ አደገኛነቱን መናገር አይከብድም። ኢትዮጵያ ውስጥ የፖለቲካ ግጥሚያ የሚያስከፍለው መሰዋትነት እንደ ስፖርቱ ላብ ሳይሆን ደምን መሆኑ ከባድ ያደርገዋል። እስቲ በጥቂቱ ስለ ሐይማኖት እና ዘር እንመልከት።

ሐይማኖት፡-

ሐይማኖት ማለት የማይታየውን እግዚአብሔር እንደ  አዩት አድርጎ ማመን ነው። እግዚአብሔር የማያዳላ  ፈራጅ እና ታማኝ አምላክ ነው። አለማትን ፈጥሮ በውስጣቸው የሚኖሩትን በእኩል የሚያስተዳድር ድንቅ አምላክ ነው። ለደጉም ለክፉውም፣ ለጻድቁም ለሃጣኑም፣ ለሚያምነውም ለማያምነውም፣ ለትልቁም ለትንሹም፣ የአምላክነቱን ጸጋ ለሁሉም ሳያዳላ እኩል  ይሰጣል። እግዚአብሔር ፀሐይን ስሙን ለሚጠራውም ለማይጠራውም እኩል ያወጣል፣ እግዚአብሔርን ለሚያምኑም ሰይጣንንም ለሚያምኑ እኩል ዝናብ ያዘንባል፣ የአየር ስጦታንም ለሰውም ለእንስሳም እኩል ይሰጣል፣ እግዚአብሔር የነጻነት አምላክ እንደሆነ እንረዳለን። ደግ ብቻ ይኑር ክፉው ይጥፋ፣ የሚያምነኝ ብቻ ይቅር ሌላይ ይሙት፣ የሚል ህግ በእግዚአብሔር ዘንድ የለም። እግዚአብሔር ሁሉን ማድረግ የሚችል ሆኖ ሳለ የማንንም እገዛ የማይፈልግ ሆኖ ሳለ በተፈቀደልን እድሜ በነጻነት እንድንኖር ፈቅዶልናል። ውሃም እሳትም ተቀምጦልሃል እጅህን ወደፈለገው  ክተት ብሎ ለሰው ልጆች የነጻ ምርጫ አስቀምቷል።

ውሃ ማለት፡- እምነትና ስራን አዋህደህ መገኘት ሲሆን እንዲህ ይገለጻሉ። ደግነት፣ የዋህነት፣ ፍቅር፣ ራስን መግዛት፣ ታዛዝነት፣ ባልንጀራህን እንደራስህ አድርገህ መውደድ። እነዚህ የሰራ መልካም ሰው በማታልፈዋ አለም በደስታ የሚያኖሩ ሲሆን…

እሳት የተባለው ደግሞ ጥል፣ ክርክር፣ መለያየት፣ አድመኝነት፣ ቁጣ፣ ክፋት፣ መግደል፣ ባልንጀራህን አለመውደድ የመሳሰሉት በዚህም አለም በማታልፈውም አለም ደስታን የማናገኝበት ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ በሐይማኖት ያለን አመለካከት ከፍተኛ ነው። በክርስትናውም በእስላሙም ሐይማኖታቸውም የሚወዱ ያሉባት ህዝብ ናት። ታዲያ ሐይማኖቱን የሚያከብር ማን ነው? እውነት በመናገር በፍቅር በማኖር የእግዚአብሔርን መንግስት እንዲወርሱ ከማድረግ ይልቅ ጥላቻንና ክፋትን እያስተማርን ለሌላው መጥፋትን የምንመኝ ስንቶቻችን ነን? በሐይማኖታችን የሚፈቀደው የታመመን በጸሎት ማዳን፣ የተጣላን ማስታረቅ፣ የተራራቀን ማቀራረብ፣ ስለሰው ሐጥያት መናገር ሳይሆን ስለራስህ ሐጥያት ማሰብ፣ ሰውን ከክፉ ስራው ወደ በጎነት መመለስ እንጂ ውድቀቱንና ጥፋቱን መመኘት በእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ የለውም።  ሰው ሆይ እግዚአብሔር ዋጋ ከፋይ ነው። መልካም የሰራ ገነትን ክፉም የሰራ ሲኦልን የሚያስገባ በነፍስም በስጋ ላይ ስልጣን ያለው እግዚአብሔር ስለሆነ በሰራነው ስራ ዋጋችንን ለመቀበል ተዘጋጅተናል ማለት ነው። ዋጋም ከፋዩ እግዚአብሔር ነው።

ዘር፡-

የሰው ዘር በሙሉ ከአዳም እና ከሄዋን እንደተገኘ በሁሉም በተ እምነት አስተምሮ ውስጥ እንዳለ የታወቀ ነው። ይህም እስከ ጥፋት ውሃ ድረስ ማለትም እስከ ኖህ ዘመን ድረስ ከቆየ በኋላ የሰው ልጅ በሰራው ክፋት እግዚአብሔር ተቆጥቶ ከምድር የሚፈልቅ ውያ ከሰማይ የማያባራ  ዝናብ  ምድርን አጥለቅልቆ በውስጧ ያሉትን በሙሉ በሐጥያታቸው ምክንያት ሲጠፉ መልካሙ ሰው የነበረው ኖህና ቤተሰቡ ከእንስሳቱ ሁለት ሁሉት አድርጎ በኖህ መርከብ ከእግዚአብሔር ቁጣ ከመጣው የጥፋት ውሃ በመትረፋቸው የሰው ዘር ሊቀጥል ችሏል። የኖህ ልጆችም ሴም፣ ካምና፣ ያፌት ይባላሉ። ዘፍጥረት 10+1-32

ሴም፡- ኤላም፣ አሦር፣ አርፋክስድ፣ ሎድ፣ አራም፣ ቃይናን ስድስት ልጆችን ወለደ።

ካም- ኩሽ፣ ምስራይም፣ ፍጥ፣ ከነዓን አራት ልጆችን ወለደ።

ያፌት፡- ጋሜል፣ ማጎግ፣ ማዴ፣ ያህያን፣ ያልሳ፣ ቶቤል፣ ሞሳሕ፣ ቴራስ ስምንት ልጆችን ወለደ።

እነዚህ የኖህ ልጆች አሁን ላለው የዘር  መጠሪያ መሰረቶች ናቸው።

በሴም፡- ሴሜቲክስ የተባሉ የኖህ ልጅ ብዙ የምድራችን ግዛትን ላይ በመስፈር መጠሪያ የያዘ የአዳም ዘር ሊጠራበት ችሏል።

በኩሽ፡- ኩሸቲክስ የተባሉ የኖህ የልጅ ልጅ ብዙ የምድራችን ግዛትን ላይ በመስፈር መጠሪያ የያዘ የአዳም ዘር ሊጠራበት ችሏል።

በያፌት፡- ያፌታውያን የተባሉ የኖህ ልጅ ብዙ የምድራችን ግዛትን ላይ በመስፈር መጠሪያ የያዘ  የአዳም ዘር ሊጠራበት ችሏል።

እንዲህ እንዲ እያለ  የሰው ልጅ በሙሉ መጠሪያውን እያበጀ ሊመጣ ችሏል። ወደ ኋላ ከተጓዝን ሁሉም  የኖህ ልጆች ናቸው። ወደ መጀመሪያው ከተመለስን ደግሞ ሁሉም የአዳም ዘር መሆናቸውን እናውቃለን። ኢትዮጵያ ውስጥ ከሰማኒያ ሁለት ያላነሱ ቋንቋዎች ይነገራል። ሁሉም ቋንቋዎች ግን ገላጪነታቸው እኩል ነው። ቋንቋ ያስፈለገበት ዋናው ቁም ነገር ሰዎች ይግባቡበት ዘንድ ነው። ለምሳሌ ገመቹ፣ ሃጎስ፣ ደስታ የሚሉትን ስሞች ብንወስድ በተለያዩ  ቋንቋዎች አንድ አይነት ትርጉም ያላቸው ገላጭ ስሞች ናቸው።  ለገመቹ፣ ለሃጎስ እና ለደስታ  ልንሰጣቸው የሚገባ ክብር እና ቦታ እኩል መሆን አለበት። እንዲህ ካልሆነ ግን ከላይ በሐይማኖት ትንታኔዬ እንዳስቀመጥኩት ሐጥያት ሆኖብን ከሰው ጋር ብቻ ሳይሆን ከአምላክ ጋር የሚያጣላ ስለሆነ ለሁሉም ተናጋሪዎች እኩል ክብር ልንሰጥ ይገባል። ቋንቋዎች በተናጋሪው ዘንድ ተወዳጅነት ስላላቸው ሁሉም ሊያከብራቸው እና ሊረዳቸው እንዲሁም ክብርም ሊሰጣቸው ያስፈልጋል። ስለ ሌላው ማሰብ ስሌላው መጨነቅ የሌላውን ቋንቋ እና ወገንተኝነትን መውደድ ተገቢ ነው እንዲ ሲሆን ባልንጀራህን መውደድ የሚለው የእግዚአብሔር ቃል ተፈጻሚነት ያገኛል።

ባጠቃላይ ወያኔ የፈጠረው እና ያዘጋጀው ሜዳ በቀላሉ የሚታይ ጉዳይ አይደለም። ወደዚህ ሜዳ  በሦስት መንገድ ይገባሉ፡-

አንደኛው በግድ ሁለተኛው በጥቅም ሶስተኛው ባለማወቅ። ዛሬ የምንመለከተው ሃቅ ይሄ ነው። ወደ ወያኔአዊ ሜዳ የመግባቱ እና የማስገባቱ ተግባር ክፍተኛ ስራ እየተሰራ ያለው በወያኔዎች ሲሆን  ተጠቃሚዎችም ራሳቸው ናቸው። የሐይማኖት አባቶች በክርስትናውም በእስልምናውም በዋቄ ፈናም በሌላም ያላችሁ እውቀት እና ችሎታው ያላችሁ በሙሉ ምዕመናኖቻቹህን ወደዚህ የጥፋት ሜዳ እንዳይገቡ ንገሯቸው። ስለ ባልንጀራ መውደድ እና ፍቅር አስተምሯቸው። እኛ ክፉ መንግስ እንጂ ክፉ ህዝብ የለንም። ወያኔ በዘረጋው የክፋት ሜዳ ላይ እንዳይገቡ መንጋዎችን ጠብቋቸው።

በዘር ጉዳይ ወያኔ የዘረጋው የጥፋት ሜዳ እንደሆነ ለገመቹም፣ ለሃጎስም፣ ለደስታም ለሌሎችም በቋንቋቸው ንገሯቸው። የኛ ጠላት ገመቹ፣ ሃጎስ፣ ደስታ ሳይሆን… ሐይማኖትን የማይፈራ፣ ዘርን የማያከብር፣ ለወገኑ ግድ የሌለው፣ ወገን ከወገኑ፣ ዘርን ከዘር፣ ለማጫረስ  የሚሰራውን  ወያኔን እንደሆነ አሳውቋቸው። ወደ ወያኔ ሜዳ የምንገባው ወያኔን ለመምታት እንጂ ሌላ እንዳይሆን አሳስቧቸው። ይህንን ስናደርግ ለሐይማኖታችን ለወገኖቻችን በመድረስ በአገር ላይ የተቃጣውን ጥፋት በቀላሉ ማስቆም እንችላለን። ይህ ከራ ረቢ ነው። አዎ መልካምነት የእግዚአብሔር መንገድ ነው።

ከ-ከተማ ዋቅጅራ

29.03.2015

Email- waqjirak@yahoo.com

The post ፖለቲካ፣ ሐይማኖት፣ ዘር፣ በሰው ልቦና ውስጥ። appeared first on Zehabesha Amharic.

የሰማያዊ ፓርቲ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ እየተካሄደ ነው

0
0

የሰማያዊ ፓርቲ የጠራውን ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ መንገድ ለማስቀየስ የሞከረው ወያኔ አልተሳካለትም::
የሰማያዊ ፓርቲ የጠራውን ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ መንገድ ለማስቀየስ የሞከረው ወያኔ አልተሳካለትም::

semawi party demo 2\

semawi party demo

የ‹‹ነፃነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› ዝግጅት

 

v

1

12

2

8semawi party demo 6

3 6 7 4 5

Semawi party dem011

ፖሊስ ሰልፈኛው ወደ ቤተ መንግስት እንዳያልፍ ሲያስቆም!

 

semawi party demo 4

ፖሊስ ሰልፈኛውን ሲያስቆም!

semawi party demo 5    semawi party demo 3

demo12

ፖሊስ ሰልፈኛውን በቤተ መንግስት በኩል እንዳያልፍ አስመልሶታል፡፡

semawi party demo 7

The post የሰማያዊ ፓርቲ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ እየተካሄደ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.


አባይ አባይ። ዳዊት ዳባ

0
0

Friday, March 27, 2015

ኬንያ ስደት ካንብ ውስጥ ልጆች ኳስ ተቧድነው ይጫወታሉ። አሊ ለብሩክ አቀበለው። ብሩክ ወደጎል መታት።  ኡመት በቀላሉ ያዛት። ኡመት ለጋ አሁን ኳሷ ጅግሳ ጋር ናት:: ጥሩ አድርጎ ለገብሬ አቀበለው። ገብሬ ደስ በሚል አብዶ ሰርቶ ተከላካዩን ደንፎን አለፈ። አሁን ገብሬና ግብ ጠባቂው ጆሬጌ ብቻ ነው ያሉት። ገብሬ ገብሬ ብቻውን ነው፤ አደገኛ ሁኔታ ነው። ገብሬ መታ ። አይይ ለትንሽ፤ ለትንሽ።  ኳሷ የግቡን እንጨት መታ ወደውጪ ወጣች።

ከተመልካቾቹ መሀል ከድጃ የኔ ነው። የኔ ነው እያለች ወደኳሷ እሮጠች። ሌሎች ተመልካቾችም ተከትለዋት እሮጡ። ከድጃ ከኳሷ ወስጥ የሆነ ነገር ደስ እያላት መዛ አወጣችና ኳሷን ወረወረችላቸው። ከዛም የኔ ነው በቀጣይ ኳሱ ውስጥ የሚገባው ጭቅጭቅ በሌሎቹ ተረኞች መሀል ጠብ ሆነ። ከድጃ የስልኳ ቻርጀሯ አልቆ ስንት ቀኗ  ፍሴ ቡክ ከገባች።ያኔውኑ  ስልኳ ላይ ገጥማ ቻርጅ ማድረግ ጀመረች። ጓደኞቿ ትግስት፤ ፋጡማና ሌንሳም የነሱንም ስልክ ቻርጅ ለማድረግ የሚበቃ የተጠረቃመ ሀይል እንዳለው ስለሚያውቁ አብረዋት ተደሰቱ።

ግድቡን በሚመለከት ሰብሰብ ባለ መንገድ መነሻ ስምምነት ተብሎ በየሜዲያው ላይ የያነው እውነተኛው ስምምነት ነው ወይ?። ወይስ   እንደአየር ጥቃቱ የውሸቱ ነው። ይህን እንድል ያስቻለኝ ጠንካራ ተቃውሞ እየሰማው ስላልሆነ ነው። ስምምነቱ እኔም ልረዳው በምችል ቀላል በሆነ እንግሊዘኛ የተፃፈ ነው።  በእርግጥም የእውሸቱ ቢሆን ይሆናል። አንብቤው የእውሸቱ በሆነ ስል ነው የፀለይኩት። ምክንያቱም  አባይን ውሀ ግብፅ ውስጥ በረዶ አድርገው ቤት ቢሰሩበት፤ ቢመርዙት ፤ ብቻ ያሻቸውን ቢያደርጉት ስምምነት በተባለው ዶሴ ውስጥ በሙሉ እኛ ይህን ማድረጋቸው በዚህ መልክ ጎድቶናል ብለን ልንከስም ሆነ ልንከራከር የምንችልበት መንገድ ባስበው ባስበው አልታየኝ አለ። ስምምነቱ እኛንም ግብፅንም ሱዳንንም በጋራ የምንገዛበትና ተጠያቂ የሚያደርግ ቢመስልም አንድና አንድ በሆነ ሁኔቴ ኢትዬጵያ ማድረግ፤ አለማድረግ፤ መውሰድ ያለባትን ጥንቃቄ በሚመለከት የተጣለባት ግዳጅ ሆኖ ነው ያገኘሁት።

ግድቡን ለኤሌክትሪክ ማመንጫነት ብቻ ለመጠቀም እንደሆነ እንደተፈራው በስምምነቱ ተካቷል። ከበፊቱም የተገነባው ጠረፍና ለእርሻ የሚሆን መሬት የሌለበት ቦታ ላይ ስለሆነ ለመሰኖ አገልግሎት ለማዋል እስቸጋሪ እንደሚያደርገው አካባቢውን በሚያውቁ ዜጎች  ሲገልጽ ነበር። በእርግጥ ወያኔዎችም ግድቡን ከኤሌክትሪክ ማመንጫነት ውጪ ለሌላ አገልግሎት የማይውል መሆኑን ቀድሞም አልደበቁም። ማንንስ ፈርተው ይደብቃሉ። ይህም ሆኖ ይገደብ እንጂ ወያኔዎች ለዘላለም አይኖሩም። ወደፊት  ወሀውን በቦይ ወደሗላ በመመለስ ለመስኖም ሆነ ለሌላ አገልግሎትም ለመጠቀም እንችላለን ተብሎም ተስፋ ተሰጥቶም አንብቤያለው። አሁን  እድሜ ለወያኔ ግድቡ እንጂ ውሀው የኛ ባልሆነበት ሁሉም ነገር በስምምነቱ እልባት አግኝቷል።

ውሀውን መከልከላችን ሳያንስ ተንከባክበንና አጣርተን ግብፆችን ማጠጣት ተስማምተን የፈረምንበት መሆኑ  እንዳለ “የኤሌክትሪክ ሀይል “ ተብሎ የሚደሰኮርበት እራሱ በቅጡ አልተመረመረም ባይ ነኝ። ወያኔዎቹን ትተናቸው ሁላችንም በይበልጥም  ሙህራኖቻችን ያላዩት ስለዚህም ያለነሱት ወና ችግር ያለ ይመስለኛል። ስብሰለሰልበት ከጀመረ ቆይቷል። ግድቡን በሚመለከት ሲነሳ የነበረው ስጋት በድህነት ከአለም አገሮች ጠርዥ ላይ ያለች አገር ለአንድ ግድብ ብቻ ይህን ያህል የአገር ሀብት አሟጣ ማፍሰስ በብዙ ጎኑ ይጎዳናል። ከተገደበና ሀይል ማመንጨት ከጀመረም በሗላም ይህ ግድብ  ከፍተኛ ወጪ ያለው ነው። ግድቡ መጨቆኛ፤ በዜጎች ዘንድም ለአባይ ካለ ጥልቅ መቆርቆር ፈቅዶ መጨቆኛም ሆኗል  የመሳሰሉ ስጋቶች ነበሩ።

የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጨትን በሚመለከት በአለሞያም ባንሆን፤ የጠለቀ እውቀቱም ባይኖረንም ከመረጃ የራቅን ካልሆንና ሜዲያዎችን የምንከታታል ከሆነ በርካሽ ማመንጨትንና  መጠቀምን  በሚመለከት በሚቀጥሉት አስርና ሀያ አመት አለም ምን አይነት ገፅታ እንደሚኖረው መገመት አይከብድም። ተግባር ላይ ውለው ልናያቸው የሚችሉትን የተሻሉ የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ አማረጮች ብዙ ናቸው። ኤሌክትሪክ በምን ደረጃ በቀላሉ ሊዳረስ እንደሚችል። ምን አይነት ዋጋ ሊኖረው እንደሚችል መገመትም እንዲሁ ከባድ አይደለም።  በቀላሉ በቀጣይ እንደሞባይል ስልክ የፀሀይ ብርሀንን የሚሰበስበው ፓናል  የአለም ህዘብ ሁሉ ይኖረዋል። አይደለም ህንፃዎች ላይ በየጎጆ ቤቱ ላይ የምናየው ዲሽ የሚሆን ይመስለኛል። አሁን ባለው ገበያ እንኳ በምኖርበት አገር ሰዎች ከ$300 እስከ $1000 ዶላር ባልበለጠ ወጋ  ጣርያቸው ላይ ፓናሉን በመግጠም የኤሌክትሪክ ፍጆታቸውን እየሸፈኑ ነው። እኔ እራሴ $29 በፀሀይ ብርሀን የሚሰራ መብራት ለቤተሰቦቼ አገር ቤት ልኬላው። አንዴ ጨክኜ ፓናሉን ባስገጥም ደግሞ ከገቢያቸው አልመጣጠን ብሎ ከሚማረሩበት ወራዊ የመብራት ክፍያ ይገላገላሉ። በፀሀይ ብረሀን የሚሰራው መብራቱ የ$19 ገበያ ላይ ነበር። የኤሌክትሪክ ሀይል ከንፋስ ከቆሻሻ፤ ከኒኩለር ለዛውም ከመጨረሻው ዝቃዥ መጣያ እየጠፋ ሲቸገሩበት ከነበረው ሳይቀር መጠኑ እጅግ ትልቅ የሆነ ማመንጫነት ተችሏል።

ከፀሀይ ብርሀን የሚገኘው የኤሌክትሪክ ሀይል ይህ በትልቅ እንዱስትሪ ደረጃ የሚሰራም አይደለም። “ ጁአካሊ” በኪሲዋሊ። “በጥቃቅንና አነስተኛ  ሰዎቻችን በሚሉት  በየጎጆ ቤቱ ላይ ሊገጠም የሚችል ነው። ዛሬ ዲሽ የሚገጥሙ ሰዋች ፓናል የሚገጥሙ ይሆናሉ። ኦባማ በቀን ውስጥ ስንት ቤቶች ነበሩ ከፀሃይ ብረሀን ከሚገኝ ኤሌክትሪክ ለማመንጨትና ፍጆታቸውን ለመሸፈን ይቀየሳሉ ያለው?። አሁን አሁን የመንገድ መብራቶች፤ አፓርትመንቶች፤ የንግድ ቦታዎች ፤ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የኤሌክትሪክ ፍጆታቸውን ከፀሀይ ብርሀን እያገኙ መሆኑን ዞር ዞር ሲሉ ትኩረት ሰጥቶ ማየትን ብቻ ነው የሚፈልገው።

በቅርብ አሜሪካኖች የአፍሪካ መሪዎችን በሙሉ በትእዛዝ ጠርተው  በዋናነት ቃል የገቡላቸው በሉት ያስሟሟቸው ሀይል በማመንጨት አፍሪካ ላይ መዋለንዋይ ሊያፈሱ ነው። ለአፍሪካችን ተጨንቀው ያበረከቱት ቾሮታ።መሪዎቹ በአስቸኳይ የተጠሩበት ዋናው ጉዳይ ይህው ነው። አሜሪካኖች በቀላሉና በርካሽ የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጨት እንደሚቻል አውቀውበታል። ጠቅላላ አፍሪካ ገና ጭለማ ውስጥ ነው ያለው። ከዚህ በላይ ገንዘብ የሚዛቅበት አውድማ መቼም የለም።  መቼም አምስትና አስር ቢሊዬን ብር እያወጡ ግድብ ገድበው አፍሪካን ብረሀን በብረሀን ሊደርጉ ነው ቆርጠው የተነሱት ብለን የምናስብ አንኖርም።

ግድቡ አለቀ እንበል። ለኛ ስንት ዘመን ስንመኘውና ስንዘፍንለት የነበረ  ከአባያችን የተገኘ ስለሆነ በግዳጅም ጭምር ገበሬው ሳይቀር መብላት ትቶ መብራት ይኑረው። ለኬንያ፤ ሱዳንና ጅቡቲ ለሌሎችም አገሮች እንዴት በአለም ገበያ አወዳድረን በቅናሽ እንዲገዙን እንደምናደርግ የሚታይ ይሆናል። አፍሪካዊው አንዴ ሶስት መቶ ዶላር ከፍሎ ለዛውም ላንድ አንፖል ቢበዛ ለፍሪጅ በቀላሉ ኤሌክትሪክ ማግኘት እየቻለ በየወሩ ለመብራት ለምን ይከፍላል። የትኛው አፍሪካዊ መንግስት ለዛውም መንግስት ሳይገባበት ዜጋው እራሱን ችሎ ሊያደርገው ሲችል በየወሩ የውጪ ምንዛሪውን አሟጦ ለኛ እየከፈለ ነው የሚያበለፅገን። በጭራሽ የማይሆን የሞኝ ሀሳብ ነው። ምን አለ በሉኝ ሁሉ ባለ መብራት የሚሆነው ደግሞ እኛ ላባችንና አንጡራችንን ጠብ አድርገን አባይን ገንብተን በምንጨርስበት ጊዜ ጋር እኩል ነው።

ለማንኛው በመጪው አስርና ሀያ አመት በሗላ ኤሌክትሪክ ሳይሆን እራሱ “ውሀው” ነው መዳረሱ አለምን እያስጨነቀ ያለው። በቀጣይ ያአለምን ፀጥታ የሚፈታተነው ነዳጅ ዘይት ሳይሆን ውሀ መሆኑ ብዙ ተብሎበታል። ውሀ የማያልቅ የማይመስለን ተሳስተናል። አላቂ  ሀብት ነው። ይሄ  ስምምነት ደግሞ አይደለም ከግድቡ ከገባር ወንዞችም በጣሳ ቀድተን ስንጠጣ ግብፅና ሱዳን አዩን አላዩን እያልን እንዲሆን የሚያደርግ ነው።  አንዴ ጉዶች ነግሰውብናል። ሊያውም የሚያደባብን። ወገን ለራሳችን እንወቅበት። ምን ማድረግ እንደምንችል ባላውቅም። ዝም ግን አንበል።

comment pic

 

The post አባይ አባይ። ዳዊት ዳባ appeared first on Zehabesha Amharic.

በየመን ኢትዮጵያውያኖች በጭንቅ ላይ ናቸው * ግማሾች እንቅልፍ አጥተው ነው የሚያድሩት…

0
0

ግሩም ተ/ሀይማኖት (ከየመን)

ረቡዕ ሌሊት 8፡30 ላይ የተጀመረው የአየር ድብደባ አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ የመን ነዋሪ የሆነ ሁሉ በፍርሃት ርዷል፡፡ በተለይ በትላንትናው ሌሊት የነበረው የአየር ድብደባ ከፍተኛ ስለሆነ ህዝቡ ላይ የጣለው ፍርሃት ከወትሮው የተለየ ነው፡፡ “በሁቲይን አማጽያን ሚሊሻ ላይ የተጀመረው የአየርጥቃት አሁንም በድርድሩ ካልተስማሙ ወይ ሰነዓ ከተማን ለቀው እስካወጡ አያቆምም!” ሲሉ የሳዑዲ አረቢያ ንጉስ ሰልማን ቢን አብድልአዚዝ ገልጸዋል፡፡ ይህን አባባላቸውን ተከትሎ እግረኛ ሰራዊትም ሊንቀሳቀስ መሆኑ እየተገለጸ ነው፡፡ 20.000 እግረኛ ወታደር ተዘጋጅቶ ድንበር ላይ መሆኑን የየመን መገናኛ ብዙሀን እየዘገቡ ነው፡፡ ከዚያ በፊት ተጀምሮ የነበረውን ድርድር እንዲቀበሉ ለሁቲይን አማጺዎች ከትላንት ወዲያ የ3 ቀን እድሜ ቢሰጣቸውም አልተቀበሉትም፡፡
People gather at the site of an air strike at a residential area near Sanaa Airport
በሳዑዲ ሰብሳቢነት የአረብ ሊግ ሀገራት መንግስታት በየመን ጉዳይ ለመመከር ግብጽ ሻርማ ሸኸ ተሰብስበው ነው ያሉት። በዚህ ስብሰባ ላይ የአየር ጥቃቱ የዘመቻ መሪ ሀገር የሳዑዲ አረቢ ንጉስ ሰልማን ሀቲይን የተባሉት አማጽያን ለቀው እስኪወጡና የመን እስክትረጋጋ ድረስ የተጀመረው ጥቃት ቀጣይ እንደሆነ ገልጸዋል በማለት የየመኑ ቶውራ ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ በዚህ ስብሰባ ላይ የየመኑ መሪ አብድረቡ መንሱር ሀዴ ተገኝተዋል፡፡ ህዝቡ ግን ሀገራችንን እያስደበደበ ያለው ፕሬዘዳንታችን ነው በማለት ጥስ እየነከሰባቸው ነው፡፡ የቀድሞው ፕሬዘዳንት አሊ አብደላ ሳላ ድርድሩን እንደሚቀበሉ ቢገልጹም ተቀባይነት ያገኙ አይመስልም፡፡

ዛሬ ሌሊት በሳውዲ የተመራው የአስሩ ሀገራት ህብረት ጦር በሰንዓ ፈጂ አጣን የተባለው ቦታ ጋራ ላይ የሚገኘው ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ያለ የብላስቲክ ሚሳየል ክምችት ማውደሙ ታውቋል፡፡ ይህ የመሳሪያ ክምችት በተመታበት ወቅት መላ ከተማው የተርገደገደበት የመሬት መንቀጥቀጥ አይነት ሁኔታ ነበር፡፡ አንዳንድ ህንጻዎች መስታዎታቸው ሁሉ ርግፏል፡፡ ነዋሪው ሲነጋ እንቅልፍ አጥቶ መደሩ ዋነኛው ርዕስ ነበር፡፡ በተለይ ስደተኛ ኢትዮጵያዊን ከፍተኛ ፍርሃት ተውጠን እንዳለን በርካታ ያናገርኳቸው ወገኖቼ ገልጸውልኛል፡፡ በእርግጥ ሌላውስ ወገን የመን ያሉ ኢትዮጵያዊያንን እንዴት እያሰባቸው ይሆን?

የተመታው ካምፕ ላይ የሚቃጠለው መሳሪያ ፍንዳታም ከፍተኛ ነበር፡፡ ከሌሊቱ 8፡20 ጀምሮ ጠዋት ድረስ እሳቱን ለማጥፋት ርብርብ ነበር፡፡ የሁቲይን አማጺያን ድብደባውን በዝምታ እያዩት አይደለም፡፡ ከየአቅጣጫው በአየር መቃወሚያ ምላሽ ይሰጣሉ፡፡ እንደ አባባላቸው ከሆነ የአየር ጥቃቱን ከሚያደርሱት ጀቶች እስካሁን ሁለት መምታታቸውን ተናግረዋል፡፡ በዛሬው ሌሊት ሰነዓ ላይ ድብደባው ቀነስ ቢልም ሁዴዳና ሌሎች ደቡባዊ የመን ላይ ጠንከር ያለ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ሁቲይኖቹም ከየአቅጣጫው የሚደረገውን ጥቃት ለመከላከል ሙከራቸው በዛሬው ሌሊት ቀንሶ ታይቷል፡፡ ሰነዓ ያለ ኢትዮጵያዊ በጭንቅ ውስጥ ሲሆን አደን የተባለው ሁለተኛ ከተማ ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያዊን በከፍተኛ ሁኔታ እያነቡ ነው፡፡

The post በየመን ኢትዮጵያውያኖች በጭንቅ ላይ ናቸው * ግማሾች እንቅልፍ አጥተው ነው የሚያድሩት… appeared first on Zehabesha Amharic.

የኮሜዲያን ዳንኤል ቁንጮ ቀብር ስነስርዓት ተፈጸመ

0
0

(ዘ-ሐበሻ) ታዋቆው ኮሜዲያን ዳኒ ቁንጮ በ37 ዓመቱ ማረፉን ዘ-ሐበሻ ትናንት መዘገቧና የቀብር ስነ ስር ዓቱም ዛሬ እንደሚፈጸም መዘገባችን አይዘነጋም::
daniel kuncho
ዳንኤል ቁንጮ ከእናቱ ወ/ሮ አስራት ሰቤ እና ከአባቱ ወልዴ ኪሮ በ1970ዓ.ም አዲስ አበባ 4ኪሎ – ፊት በር ተወለደ፡፡ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በዳግማዊ ምኒሊክ ተማረ፡፡ ትያትር በተለያዩ ክበባት ተምሯል – ሰዓሊም ነበር፡፡

ዳ ኤል ቁንጮ – በተለያዩ ክለቦች በዲጄነት ሲያገለግል ከነዚህም ውስጥ ፒያዛ – በአካልፀ ሆቴል እና 22 ማዞሪያ – ሰገን ሆቴል ይጠቀሳሉ፡፡ ኮሜዲያን ዳኒ ቁንጮ በርካታ የኮሜዲ ሥራዎቹን አበርክቷል፡፡

እናቱ ወ/ሮ አስራት ሰቤ ልጃቸው በታመመበት ወቅት ወደ ሚዲያ ቀርበው ‹‹እባካቹ ልጄን አትርፉልኝ?›› ሲሉ ተማጽነው ነበር፡፡ ሐሙስ ዕለት ተክለሃይማኖት ሆስፒታል ለህክምና ገባ፡፡ ትላንት ቅዳሜ መጋቢት 19 ቀን 2007ዓ.ም በአደረበት ህመም በ37 ዓመቱ ያረፈው ዳን ኤል ቀብሩ – ዛሬ ከቀኑ 6፡00 ሰዓት በሳሊተ ምህረት ቤተ-ክርሲቲያን (ጉርድ ሾላ) ወዳጅ ዘመዶቹና የሙያ አጋሮቹ በተገኙበት ተፈጽሟል::

The post የኮሜዲያን ዳንኤል ቁንጮ ቀብር ስነስርዓት ተፈጸመ appeared first on Zehabesha Amharic.

ዘመቻ ”ወሳኙ ማዕበል”እና አበይት ክንውኖቹ –ነቢዩ ሲራክ

0
0

የመረጃ ግብአት .. በ4ኛው ቀን ዘመቻ … ( Update )

Nebiyu Sirak* ትናንት ቅዳሜ መጋቢት 19 ግብጽ ሻርማ ሸክ ተሰብስበው የነበሩት 22 የአረብ ሊግ ሀገራት መራሄ መንግስታት በ26 ኛው መደበኛ ስብሰባ የየመንን ጉዳይ በሰፊው ተነጋግረውበታል

* መራሔ መንግስታቱ የሁቲ አማጽያን በኃይል ከያዘው ስልጣን ለማስወገድና ህጋዊውን የፕሬ አብድልረቡ መንግስት ወደ ቦታው ለመመለስ ተስማምተዋል !

* የሳውዲው ንጉስ ሰልማን ” ዘመቻው ግቡን እስኪመታ አያቆምም !” ሲሉ የግብጽ ፕሬ አል ሲሲ በበኩላቸው የጽንፈኝነትን መንሰራፋት በማውሳት በአረብ ሀገራትን አደጋና ከኢራን ትንኮሳ ለመታደግ ጥምር የጦር የአረብ ሀገራት ሰራዊት እንደሚያስፈልግ በስብሰባው ላይ በአጽንኦት ተናግረዋል

* ጉባኤው በአረብ ጥምር የህብረት ጦሩን ጉዳይ ከመከረ በኋላ በስብሰባው መዝጊያ የአብ ሊግ ዋና ጸሃፊ ነቢል አል አረቢ ባሰሙት የአቋም መግለጫ ከዚህ ቀደም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ያቀረቡት ረቂቅ ህግ ተጠንቶ በአጠቃላይ ጉዳይ በአንድ ወር ውስጥ ተገናኝተው በመምከር ታሪካዊ ያሉትን የህብረት ጦሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመመስረት እቅድ መያዙን አስታውቀዋል

*  የኩዌትን አሚር ጨምሮ የተለያዩ አረብ ሀገራት ኢራን የአካባቢውን ሀገር ሰላም ለመንሳት በተዘዋዋሪ የምታሳየውን ተደጋጋሚ ፍላጎት ተቃውመውታል

* ፖለቲካ ነውና ያልተጠበቀው ይሆናል ፣ የፍልስጥኤም መሪ ፕሬ መሀሙድ አባስ በአረብ ሊግ ስብሰባ የተገኙ ሲሆን ከኢራን ድጋፍ ያገኛል የሚባለው የፍልስጥኤሙ ሽምቅ ተዋጊ ሃማስ የአረብ ሀገራቱን አቋም የሚደግፍ አስገራሚ የድጋፍ መግለጫ አውጥቷል

* የየመንን ህጋዊ መሪ ፕሬ አብድልረቡ መንሱር አልሃዲን መንግስት ወደ ስልጣን ለመመለስ በሳውዲ የሚመራውን ዘመቻ እንደሚደግፈው ፍልስጥኤምን ነጻ ለማውጣት ጠመንጃ ያነሳው ሽምቅ ተዋጊው ሃማስ ዘመቻውን ደግፎ መግለጫ ማውጣቱ ብዙዎችን አስገርሟል

* ስድስቱ ኦማንን ሳይጨምር የባህረ ሰላጤ ሀገራትን ሳውዲ ፣ ኢምሬት ፣ ቃጣር ፣ ኩዌትና ባህሬንን ጨምሮ ዮርድያኖስ ፣ ግብጽ ፣ ሱዳን ፣ ሞሮኮ በዘመቻው ተሳታፊ ሲሆኑ ፣ ቱርክ፣  ሞሮኮ ፣ አሜሪካ ፣ እንግሊዝ ፈረንሳይ እና ቤልጅየም ድጋፍ መስጠታቸው ይጠቀሳል በአንጻሩ ሶርያ ፣ ኢራን ፣ ራሽያና ቻይና ዘመቻውን አጥብቀው ተቃውመውታል

* ኢራን የሁቲ ሸማቂዎችን በማስታጠቅና በመደገፍ ከፍተኛ ሚና እንደተጫወተች የየመን ፕሬ አብድልረቡ መንሱርና የአረብ ሀገር መራሔ መንግስታት ቢጠቁሙም ኢራን የሚቀርብባት ውንጀላ ሁሉ ” መሰረተ ቢስ ውንጀላ ነው! ” ስትል አስተባብላለች

የትዕንግርተኛው የመን ” ድብደባውን አቁሙ! ” ተማጽኖ …

* የቀድሞው የየመን ፕሬ አሊ አብደላ ሳላህ ከ30 ዓመት በላይ የመንን ሲያስተዳድሩ አቀማጥለው የደገፏቸው ፣ የአረብ አብዮት መጥቶ ሀገር የመን ስትታመስና ፕሬ አብደላ ሳላህ በአጥፍቶ ጠፊ ሲጎዱ አፈፍ አድርገው ህይወታቸውን የታደጉትንና ወደ ኋላም የመን በተቃውሞ ስትናጥና ስልጣናቸው አልረጋ ሲል መውጫ መንገድ ያበጁላቸው በቅርብ ሳውዲዎች ፣ በርቀት የባህረ ሰላጤ ሀብታም አረብ ሀገራትና ምዕራባውያን ናቸው

* ዛሬ የቀድሞው ፕሬዚደንት ከቁርጥ ቀን ደጋፊያቸው ከሳውዲ ፣ ከአረብ ሀገራትና ከምዕራባውያን በተቃራኒ ጎራ መሰለፋቸው ይጠቀሳል ፣ የቀድሞ ታዛዥ አጋራቸውና ስልጣናቸውን ሳይወዱ በግድ ያስረከቧቸውን የፕሬ አብድልረቡ መንበረ ስልጣን እንዳይረጋ እንደ ኢራን በድብቅም ባይሆን በግላጭ ሁቲዎችን በመደገፍ የቀድሞው መሪና ልጃቸው አህመድ የመንን ለዚህ ውጥንቅጥ እንዳደረሷት ይጠቀሳል

* የቀድሞው የየመን ፕሬ አሊ አብደላ ሳላህ በ26 ኛው የአረብ ሊግ የመሪዎች ስብሰባ ለተቀመጡት መራሔ መንግስታት ሳውዲ መራሹ ዘመቻ ያቆም ዘንድ ” ችግሩ የተፈጠረው በፕሬ አብድልረቡ የአስተዳደር አቅም ማነስ ነው ፣ ድብደባውን አቁሙ ፣ መፍትሔው በድርድር እንጅ በጦርነት አይደለም! ” የሚል አንድምታ ያለው ትንግርተኛ ተማጽኖ በአንድ ታዋቂ የአረብኛ ቴሌቪዥን በኩል መልዕክት አስተላልፈዋል

* የቀድሞው ፕሬዚደንት የቆየውን የሳውዲና የሀገራቸውን መልካምና ጠንካራ ግንኙነት ፣ ከ1.7 ሚሊዮን በላይ የመናውያን በሳውዲ በተለያዩ ስራዎች ተሰማርተው የመገኘታቸውን መልካም ጉርብትና በማውሳት ሳውዲ መራሹ ጦር በየመን ላይ የከፈተውን ዘመቻ ልጆቻችንና ሀገራችን እያወደመ ነው ሲሉ ድብደባው በአስቸኳይ ያቆም ዘንድ ልዩ መልዕክትን ለሳውዲ መንግስት አስተላልፈዋል

* የቀድሞው የየመን ፕሬ አሊ አብደላ ሳላህ በዚሁ ንግግራቸው የመንን በድርድር የማረጋጋቱ ስራ ቅድሚያ ይሰጠው ሲሉ የየመን ወቅታዊ ችግር በድርድር ከተፈታ በቀጣይ ምርጫ ቢደረግ እርሳቸውም ሆኑ የቤተሰብ አባሎቻቸው ወደ ስልጣን መንበር የመውጣት ፍላጎት እንደሌላቸው በንግግራቸው አስታውቀዋል

* የቀድሞው የየመን ፕሬ አሊ አብደላ ሳላህ ልጆች መካከል የጦር መኮንኑ አህመድ በሶስተኛው ቀን የአየር ላይ ድብደባ እንደቆሰሉ አንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ጠቁመዋል ። የተረጋገጠ መረጃ ነው ማለት ግን አይቻልም። ይህ በእንዲህ እንዳለ በቀድሞው የየመን አስተዳደር በከፍተኛ የጦር ኃላፊነት ያገለግሉ ከነበሩት ውስጥ የቀድሞው ፕሬዚደንት ልጅ አህመድ በሳውዲ የተመራው ጦር የዘመቻ ጥቃት ከመደረጉ አስቀድሞ የሁቲ አማጽያንን ከስልጣን ለማስዎገድ እድሉ እንዲመቻችለት ጥያቄ አቅርቦ ተቀባይነት አለማግኘቱን አል አረቢያ ዘግቦታል

የሁቲዎቻ ዛቻና የዘመቻው መምሪያ መግለጫ 

* የሁቲ ከፍተኛ ባለስልጣን አብል ሙንኢም አል ቁረሽ የሳውዲን ጣልቃ ገብነት በዚህ ከቀጠለ ሳውዲ ልትቆጣ ጠር የማትችለው ጥቃት እንሰነዝራለን ሲሉ ለኢራን አል ፋሪስ ዜና ወኪል በሰጡት መግለጫ ዝተዋል

* በሁቲዎች ዛቻና በዘመቻው ዙሪያ ትናንት መግለጫ የሰጡት በሳውዲ የተመራው የህብረት ጦር ቃል አቀባይ  ብርጋዴር ጀኔራል አህመድ አሲሪ ስለ አራተኛው ቀን የአየር  ድብደባ መግለጫ ሰጥተዋል

* ብርጋዴር ጀኔራል አህመድ አሲሪ በተለያዩ ከተሞች በዘመቻው መምሪያ በተጠኑ የሁቲ አማጽያን ወታደራዊ ኢላማዎች አልፎ ወደ ሳውዲ የመን ድንበር የጀዛንና ነጅራን ዘልቀው ጥቃት ሊሰነዝሩ የነበሩ የሁቲ ቡድን አባላት እግር በእግር  እያታሰሰ የመደምሰሱ ስኬታማ ስራ መስራቱን የዘመቻው ቃል አቀባይ አስረድተዋል

* ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጀኔራል አህመድ አሲሪ በዚሁ መግለጫቸው በሳውዲ የተመራው የህብረት ጦር በሁቲ አማጽያን እጅ የነበረውን የብላስቲክ ሚሳየል ክምችት ballistic missile stockpile በአብዛኛው ማውደሙን አስታውቀዋል

* ከየመን ሰንአ የህብረቱ የአየር ኃይል ጦር የደቡብ ከተማዋ በዳሊያ ባደረገው ወታደራዊ ይዞታዎች ኢላማ ያደረገ ድብደባ የሁቲ አማጽያን ጸረ አውሮፕላን በመተኮስ መልስ መስጠታቸውም ተጠቁሟል

* ወደ ሶስት መቶ የሚጠጉ የሳውዲ ፣ የምዕራባውያን ሀገር ዲፕሎማቶች እና የተባበሩት መንግስታት ሰራተኞችን በተለያየ ዘመቻ ሰንአ የመንን ለቀው መውጣታቸው ታውቋል

እስኪ ቸር ያሰማን  !

ነቢዩ ሲራክ
መጋቢት 20 ቀን 2007 ዓም

The post ዘመቻ ” ወሳኙ ማዕበል” እና አበይት ክንውኖቹ – ነቢዩ ሲራክ appeared first on Zehabesha Amharic.

“የስለት ልጅ ነኝ”–አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ (ከታማኝ ሾው ጋር)

0
0

በቅርቡ ወገኔ የሚለውን ተወዳጅ ነጠላ ዜማ የለቀቀው አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ ከታማኝ በየነ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ስለ ሙዚቃ ሕይወቱና ስለራሱ ሕይወት ተናገረ:: ብርሃኑ “የስለት ልጅ ነኝ” ብሏል:: ቃለምልልሱን ይከታተሉት::

“የስለት ልጅ ነኝ” – አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ (ከታማኝ ሾው ጋር)

The post “የስለት ልጅ ነኝ” – አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ (ከታማኝ ሾው ጋር) appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live