Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ ጭምብል ባጠለቁ ግለሰቦች ተደበደቡ

$
0
0

blue partyበጉጅ ዞን አዶላ ወረዳ ሰማያዊ ፓርቲን ወክለው ለክልል ምክር ቤት በዕጩነት የቀረቡት አቶ ኤልያስ ጣሂር የካቲት 25/2007 ዓ.ም ጭምብል በለበሱ ግለሰቦች ከፍተኛ ድብደባ እንደደረሰባቸው የጉጂ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪ አቶ ግርጃ ገቦ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡

በተመሳሳይ የካቲት 21/2007 ዓ.ም ቦረና ዞን ተልተሌ ወረዳ የጤና ጥበቃ ሰራተኛ የሆኑት አቶ ታሪኩ በሀይሉ ‹‹የተቃዋሚ ፓርቲ አባል ነህ›› በሚል በፖሊሶች ከፍተኛ ድብደባ ከደረሰባቸው በኋላ ለእስር መዳረጋቸውን የቦራ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አቶ ጌታቸው በቀለ ለነገረ ኢትዮጵያ ተገልጾአል፡፡ አቶ ታሪኩ በሀይሉ ስብሰባ ላይ የመብት ጥያቄ ባነሱበት ወቅት በፖሊስ ከስብሰባው እንዲወጡ ከተደረገ በኋላ ከፍተኛ ድብደባ ደርሶባቸው ለእስር መዳረጋቸውን አቶ ጌታቸው ገልጸዋል፡፡

The post የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ ጭምብል ባጠለቁ ግለሰቦች ተደበደቡ appeared first on Zehabesha Amharic.


እጩ ተወዳዳሪዎቻችን እየታሰሩ ናቸው –አምዶም ገብረስላሴ

$
0
0

ኣቶ ብርሃን ንጉስ ተክለዝጊ የተባሉ የዓረና-መድረክ የክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ ከነ ሚስታቸውና ታላቅ ልጃቸው ታሰሩ።

ኣቶ ብርሃን ንጉስ ተክለዝጊ በቖላ ተምቤን ወረዳ የወርቃ ኣምባ ምርጫ ክልል ዓረና-መድረክ ወክለው ለክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ ሁነው ቀርበዋል።

ይህ እስር የተፈፀመው በወረዳው ኣስተዳዳሪዎች፣ የሃይማኖት ኣባቶች፣ የቅርብ ዘመዶች ከውድድሩ እንዲወጡ የተሞከረው ልመናና ማባበል ሊቀበሉ ባለመቻላቸው ነው።

1545648_786839981400938_395658053806875682_nኣቶ ብርሃን ንጉስ ተኽለዝጊ በቖላ ተምቤን ወረዳ ስምረት ቀበሌ ለበርካታ ዓመታት ዋና ኣስተዳዳሪና የምሊሻ ኮማንደር ሁኖው ኣገልግለዋል። ኣስተዳዳሪ በነበሩበት ወቅት ከፍተኛ የህዝብ ፍቅር ያሳደሩ ሲሆን ከስልጣናቸው ሲወርዱም ያለ ህንዝብ ፍቃድ ከወረዳ የመጣ ትእዛዝ የተደረገ ነበር።

የወረዳው ኣስተዳዳሪዎች “.. ይህ ህዝባዊ ቅቡልነቱ ተጠቅሞ ዓረና-መድረክ እንዲያሸንፍ ያስችለዋል..” የሚል ስጋት በመፍጠሩ በማሳደራቸው በራሳቸው ትእዛዝ ዛሬ ዓርብ 27 / 06 / 2007 ዓ/ምኣቶ ብርሃን ንጉስ ተኽለዝጊ፣ ባለቤቱና ታላቅ ልጁ በጉያ እስር ቤት እንዲታሰር ኣድርገዋል።

የህወሓት መንግስት የመድረክ በኣፅቢ ወንበርታ እጩ ተወዳዳሪ የሆነው ኣቶ ወልደገብርኤል ሃይሉም “..የኣስር ወር እስር ተፈረደብህ..” በማለት ውቕሮ ወህኒ ቤት ማስገባታቸው የሚታወስ ነው።

የመድረክ እጩ ተወዳዳሪዎች እጅግ የከፋ የእስር ዛቻና እንግልት እያደረሱ ያሉ ወረዳዎች ጣንቋ ኣበርገለ፣ እምባ ኣላጀ፣ ኣፅቢ ወንበርታ፣ ቖላ ተምቤን፣ ታሕታይ ማይጨው፣ ዓዲ ግራት ናቸው።

በነዚህ ወረዳ የሚገኙ እጩ ተወዳዳሪዎቻችን ድብደባ፣ እስር፣ ወከባና እንግልት እየደረሰባቸው ይገኛል። እነዚህ ወረዳዎች ግፉ ያበዙት ብለን የገለፅናቸው እንጂ እንደ ደጉዓ ተምቤን የመሰሉ ወረዳዎችም “..ያለ የወረዳ የድጋፍ ደብዳቤት ቅስቀሳ የሚያካሂድ፣ በራሪ ወረቀት የሚያድል ሰው ካገኛቹ እርምጃ ውሰዱበት..” የሚል ትእዛዝ ለሚልሻዎች ያስተላለፉም ኣሉ።
ያሁሉ የምሊሻ የተኩስ ልምምድ ሲያካሂ የከረመው ዓረና-መድረክ ኣባላት ቅስቀሳ ሲያካሂዱ ኣልሞ ለመምታት ታሳቢ ኣድርጎ ነበር ማለት ነው።

በኢትዮዽያ ያለው የይስሙላ ምርጫው በትግራይ ያለው ሁኔታ ግን ጭራሽ የምርጫ ጭላንጭል እንዳይታይ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ።

ነፃነታችን በእጃችን ነው..!

IT IS SO..!

The post እጩ ተወዳዳሪዎቻችን እየታሰሩ ናቸው – አምዶም ገብረስላሴ appeared first on Zehabesha Amharic.

አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹ወገኔ›› የተሰኘውን ሙዚቃ እንዲቀሰቅስበት ፈቀደ

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ በቅርቡ ‹‹ወገኔ›› በሚል ያወጣውን ዜማ ሰማያዊ ፓርቲ ለቅስቀሳ እንዲጠቀምበት መፍቀዱን ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ ገልጾአል፡፡ ኤፍ ኤም 96.3 ሰማያዊ ፓርቲ ለቅስቀሳ በላከው መልዕክት ላይ በማጀቢያነት የተጠቀመበት ሙዚቃ የባለ መብቱን ፈቃድ አላገኘም በሚል የቅስቀሳ መልዕክቱን መመለሱ ይታወሳል፡፡ በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ) የሰማያዊ ፓርቲን የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ‹‹እንደገና አስተካክሎ ካልላከ ለማስተላለፍ እቸገራለሁ›› በሚል መመለሱን ለፓርቲው በፃፈው ደብዳቤ አስታወቀ፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹በ2007 ዓ.ም አዲስ ላወጡት ‹‹ወገኔ›› የተሰኘው ነጠላ ዜማ ያለውን አክብሮት እየገለፀ፣ እርስዎ በስራዎ የገለጹትና ፓርቲውም የሚታገልላት አንድነቷ የተጠበቀላት ኢትዮጵያ እንድትኖር ለሚሰራው ስራ ይጠቀምበት ዘንድ ሙዚቃውን እንዲፈቅዱልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡›› ብሎ በደብዳቤ በጠየቀው መሰረት አርቲስቱ ፓርቲው ‹‹ወገኔ›› የተሰኘውን ዜማ ለቅስቀሳ እንዲጠቀምበት መፍቀዱን ገልጾአል፡፡

አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ ለሰማያዊ በፃፈው ደብዳቤ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ‹ወገኔ› የተሰኘውን ሙዚቃዬን ለመጠቀም የጠየቀኝን ፈቃድ በሙሉ ፍላጎቴ መፍቀዴን በፊርማዬ አረጋግጫለሁ፡፡›› ሲል ገልጾአል፡፡

The post አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹ወገኔ›› የተሰኘውን ሙዚቃ እንዲቀሰቅስበት ፈቀደ appeared first on Zehabesha Amharic.

ዛሬም ታጥቦ ጭቃ … !!!! ወያኔም የሚፈልገው ይህንን እኮ ነው::

$
0
0

ትላንትና የአንድነት ሃይል ነን ሁላችን ለኢትዮጵያችን ሲሉን የነበረ ስለኦሮሞ ሕዝብ መበደል አቤት ሲባል ኦሮሞ መሆኔን ወደ ኢትዮጵያዊ መሆኔ/ሰው መሆኔ ይቀየር ብለው የሰብዐዊነት ዘመቻዎችን በጥፊ ለማላጋት የተንደረደሩ ኦሮሞ አሊያም ሌላው ብሄር ሲጠራ ጀመሩ ዘረኝነት የሚሉ አተፍታፊዎች ኢትዮጵያ ብለው በስሟ የሚነግዱ ጥቂቶች ዛሬ ላይ አማራው ይደራጅ አሊያም ይገንጠል እያሉ ማራገባቸው የፖለቲካ ስትራቴጂ አይሉት የድል ግብ ምን ያህል ማንነታቸውን ገልጸው እንዳወጡ በይፋ አይተናል::በእምነቶች ዙሪያ የሚደረጉ ትግሎችን ውስጥ ውስጡን ለማክሰም ሲራወጡ ያየናቸው አዛኝ ቂቤ አንጓቾች ድፍርስ የፖለቲካ ባህሪያቸውን አደባባይ ላይ እያስነበቡን መሆኑ ለሽሙጥ ዳርጓቸዋል::

ራሳችንን ወደ አንድነት እንምራ አምባገነኖችን ታግለን ሕዝቦችን እይመራን ነጻ እንውጣ…መስመራችን ለአንዲት ኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያን ጥርጊያ እያበጀን እሾህ እና አሜኬላ እየነቀልን ወያኔን ከነግሳንግሱ በጋራ ተባብረል በአንድነት ሃይላችን እናስወግድ የጎሳ ፖለቲካ ከቅኝ ገዢዎች የተወረሰ የመከፋፈያ እና ሕዝቦችን የመርገጫ መሳሪያ ነው እያልን ባለንበት ሰአት እየተወያየን ለትግላችን በምንተባበርበት እና የዳበረ የሰለጠነ ሃሳብ በምናፈልቅበት ወሳኝ ወቅት ላይ የወያኔን የጎሳ ፖለቲካ ልዩ መርዛዊነት ታከን ለመደራጀት ሲከፋም ለመገንተል ማሰባችን የምንሄድበት መንገድ አለማወቅ ብቻ ሳይሆን ከጭቃ ወደ እሾሃማ ሽቃ እያዘነበልል መሆኑን ልንረዳው ግድ ይላል:: ትላንት የአንድነት ሃይል ነን የሚሉ ግሳንግሶች ዛሬን ስለመገንጠል እና ስለ ጎሳዊ መደራጀት ሊሰብኩን ሲሞክሩ ምሞከራቸው ጤነኝነታቸውን እንድንጥራጠር አድርጎናል::

ወያኔ የሚፈልገው እኮ የታገለለትም አላማ እኮ ይህ ነው:: በጎሳ ምከፋፈል ማደራጀት ማስገንጠል ማገነጣጠል በይፋ በፖለቲካ ፕሮግራሙ እና ግልባጩ በሆነው ህገመንግስቱ ላይ በግልጽ ሰፍሮ ከመታየቱም በላይ ከአመት እስከ አመት የሚሰበከው በውጪም በሃገር ውስጥም ለኢትዮጵያውያን የተሰጠው የቤት ስራ ይሕው በጎሳ እንደራጅ ንገንተል የሚለው መርዘኛ ፕሮፓጋንዳ ሲሆን ህዝብንም እየለያየ የሚያፋጀው የሚያፈናቅለው የሚያሰድደው መኖሪያ አሳጥቶ የሚያንከራትተው የሚያሳስረው የሚያስገድለው ወዘተ ይኸው ከይሲ አስተሳሰብ ነው::ኢትዮጵያውያን በጋራ በአንድነት ተያይዘን የወያኔን አምባገነን ዘረኛ መንግስት እናስወግድ ብለን ከዳር እስከዳር እያስተባበርን እየቀሰቀስን ባለንበት ወቅት ላይ አደፍራሽ ሃሳቦችን በማራገብ የወያኔን የቤት ስራ ለመስራት መራወጥ ወንጀለኝነት እና የትግል አደፍራሽነት ቢሆንም የዚህ ሃሳብ ባለቤቶች ሩጫ ወንዝ እንዳማያሻግራቸው እና እንደማይሳካላቸው አስረግጠን ልንነግራቸው ይገባል::የወያኔ መደምሰስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የወያኔ ሃሳቦችን ሆኖ ቦምቦች አብረው የሚከሽፉበት ጊዜ ሩቅ አይደለም:: ድል የሕዝብ ነው::መነጣተል አሊያም መገነጣጠል ብሎም በጎሳ ፖለቲካ መደራጀት የምትሉ እናንተ በፖለቲካ እና በኢኮኖሚ እየተበደለ በገዢዎች አለንጋ ለሚገረፈው ደሃው ወገናችን እዘኑለት::

‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

Comment

The post ዛሬም ታጥቦ ጭቃ … !!!! ወያኔም የሚፈልገው ይህንን እኮ ነው:: appeared first on Zehabesha Amharic.

[የቴዎድሮስ አድሃኖም ቅሌት ጉዳይ] “ተበርቼ ሰላም!”አለ ያገሬ ሰዉ…ከ ሳዲቅ አህመድ

$
0
0

tewedros

የዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴሩ በሶሻል ሚዲያ ላይ እኔን ለቀቅ አርጉ ልጅቱ ያለችዉን ነዉ ያልኩት ለህጻን ንጹህ ህሊና እምነትን መቸር አለብን ሲሉ ያለማቅማማት ተናገሩ። የዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ከገቡበት ኪሳራ ለመዉጣት ምጸትን ሲጠቀሙ፥ ምጸትን መጠቀሙ ግድ አለን።

ትንሽ ከቴዲ ጋር እንፎጋገር።

ማረግ፣ክብር፣ፈገግታ፣ጊታር፣መዝፈን፣የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያዉም ዶክተር…አቤት አቤት ያንተ ያለህ (ያ-ሳትር-ያ-ረብ!) http://en.m.wikipedia.org/wiki/Tedros_Adhanom ዶክተር ልጅቱን ለቀቅ ያርጓት::

ይህ ስለ ልጅቱ ሳይሆን የርሶን የወደፊት አገርን የመምራት፣ጠቅላይ ሚኒስቴር የመሆን ብቃት አመላካች ነዉ።እንኳን ደስ አሎት!ሌላዉ ቀርቶ የህወሃት ቁኝጮ የነበሩት ለገሰ ነበር ስማቸዉ? መቼ አላህ ብለዉ ያዉቃሉ? መቼ ኢንሻ አላህ ብለዉ ያዉቃሉ? መቼ ገለቱማ ብለዉ ያዉቃሉ? እንደዉ እርሶ እንደ እርሳቸዉ ጫካ አልገቡም እንጂ የሚመቹ ጠቅላይ ሚኒስቴር ይሆኑ ነበር።

አዩ በህወሃትኛ ስህተት የሚታረመዉ በሌላ ስህተት በመሆኑ ችግር የለዉም።ደግነቱ ማስቀየስ የሚችል የተዋጣለት የፕሮፓጋንዳ ሰዉ የላቹም። ያዉ አትላንታ ቅንድቡን የመሳሰሉ ሰዎች ጥሩ አድርገዉ ደረጃቹን ከፍ ያደርጉታል።ሲዲ አልሽጥም ያለዉ ዘፋኝ በሙሉ መጠጊያ ማግኘቱ የ አርቲስቶቻችን ሞራል ለመጠበቅ አሌ-የማይባል ጠቀሜታ ስላለለዉ ያንድ ወቅት የሲልቨር እስፕሪንግ ሜሪላድ ጎረቤታችን (በከፊል ጀመዓችን) ከሙሴ በትር (አሳ ሙሳ) እስከ ደደቢት የጥበብ ልማትን ማስመዝገቡ እሰየዉ የሚያስብል አይመስሎትምን?

ግን ዶክተር ምን አልባት የጫካዎቹ ህወሃቶች እርሶን ማኖ ለማስነካት ይህንን ገጸባህሪ በፖለቲካ ድርሰት ደርሰዉት ቢሆንስ? ‘ያልጠረጠረ ተመነጠረ!’ ነዉ? ወይስ ከእነ ኦባማ የተኮረጀዉ የሶሽል ሚዲያ አጠቃቀም የዞረ ድምርን አምጥቶ ‘የለመዱት ልማድ ያሳዳል ከማእድ ሆነ ነገሩ?

አንዳንዴ እኮ ስለ እኛ ሳይሆን ስለወለድናቸዉም ልጆች ስንል ክብራችንን እንጠብቃለን።ዉይ!.. ልጆቻችንን አንገት የሚያስደፋ ነገር ምነኛ ከፋ።የተጠቀለሉት ጠቅላይ ሚኒስቴር ቦታዉን ከያዙ በሗላ ዘላለማዊ ክብር ምናምን ብለዉ በመናገራቸዉ በልጆቻቸዉ መተቸታቸዉን ተናግረዋል። ግን ችግር የለዉም ልጆች ከተኙ በሗላ የፌስ ቡክና የትዊተር ዘመቻ ስለሚጀምሩ ምን ችግር አለዉ?

ዶክተር በዲሲዉ ሌላኛዉ ቅንድቡ በኩል ያች የተነፈሷት የጓንታናሞ አስተያየት እርሶ ምነኛ የመጠቁ መሆኖን አመላካች ቢሆንም አንድ በምናምናዊ ሐረካት ያሳያቹት የዲሲ አካባቢ ጋዜጠኛ እርሶ ከመጠቁበት ቦታ መረጃ በሚሉት አዉጫጪኝ አዉርዶ ለመፈጥፈጥ ሳዓታት ነበር የፈጁበት። በልጅቱም ጉዳይ ላይ ለመድገም አስቦ አበበ ገላዉ ስራ ስላቀለለት ትቶታል። እባኮትን ባንዳንድ የድረ-ገጽ አስተያየቶች የሚያደርጉትን ከማድረግ አይቦዝኑ።

እርሶ እኮ የተለያዩትን ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ከተቻለ ለማዋሃድ ካልተቻለ በጋራ ጥቅም ተከባብረዉ እንዲኖሩ ለማድረግ… ያሎትን ትስስር በመጠቀም ….ሚና ያሎት ኖት። ግን በጫኮቹ ህወሃቶች መቼ እለት ያገኙት “ኤ”… “ሲ” እናዳይሆን ብዙ በሪቱዎች ከያሉበት ያምጡ። በነገራችን ላይ “ልብ ያለዉ ልብ ይበል!” የሚለዉንም ነገር ይረዱ።ለዛሬ በዚህ ይብቃ።

The post [የቴዎድሮስ አድሃኖም ቅሌት ጉዳይ] “ተበርቼ ሰላም!” አለ ያገሬ ሰዉ… ከ ሳዲቅ አህመድ appeared first on Zehabesha Amharic.

ዲ/ን ዳንኤል ክብረት፣ አቶ ኤርሚያስ ለገሰና ኢህአዴግ

$
0
0

Ermias Legesseከጀማል ሙሳ

«አክራሪ እስልምና የኢትዮጵያ ክርስትና አስቸጋሪው ፈተና» ብለህ ያዘጋጀኸውን ጥናታዊ ጽሁፍ አዳመጥኩት። አቶ ኤርሚያስ ለገሰ የሰጠህን ምላሽም እንዲሁ አነበብኩት። አንተም «ኤርሚያስ ሆይ!» ብለህ የጻፍከውን ምላሽ አንብቤ እንደጨረስኩ «ለዲያቆን ዳንኤል ክብረት የመጨረሻ አስተያየት» የሚለውን የኤርሚያስን ጽሁፍም አነበብኩት። ሁሉንም ካነበብኩ በሗላ ግን ባንተ ብቻ ሳይሆን ባገሬ መንግስትም በጣም አዘንኩኝ።

በርግጥ ኤርሚያስ ለገሰ በሰጠህ መልሶች ብዙዎችን የማውቃቸውን እውነታዎች ባገኛቸውም ካንተን ጥናታዊ ፅሁፍና የመልስ ፅሁፎች ግን አንተና የኢህአዴግ ባለስልጣናት ለኢትዮጵያ ሙስሊም ያላችሁን ትልቅ ጥላቻ ለመገንዘብ ችያለሁ። ያነሳሃቸውን ነጥቦች ስመለከት ከመጀመሪያው ጀምሮ ያቀረብከው ታሪክ ስለቁራአን ፤ስለነጃሽ ፤ስለኢትዮጵያውስጥ እስልምና ፤ለአጼ ሃንስ እለፈት ምክኒያት ሆኑ፤ሞሶሎኒ እንዃን ሳይቀር ለሙስሊም ያደላ ዕንደነበር፤የክርስቲያን ሴቶች ራሱ በሙስሊሞች እንደሚደፈሩ፤የቤተክርስተያን ቅርሶች በሙስሊሞች እንደሚዘረፉ፤ ባጠቃላይ ከድሮ ጀምሮ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ለክርስቲያኖች ፈተና እንደነበሩ፤ወደፊትም ትልቅ ጠላት መሆናቸውን፤በአገሪቱ የሂጃብ መስፋፋት፤ የመስጊዶች ፤የቁርአን ትምህርት ቤቶች ፤ የኢስላማዊ ድርጅቶች ፤የሃጅ እና ዑምራ ተጓዦች፤ኢስላማዊ መፅሃፍትና ሌሎችም የሙስሊሙ እንቅስቃሴ አንተ ከምተፈልገው ቁጥር በላይ መብዛቱ እንዳሳሰበህ ከመግለፅና በሙስሊሙናክርስተያኑ መሃከል ጥላቻን ከመዝራት ባሻገር የገለፅካቸው ሁሉ ነገሮች ከጥናታዊ ፅሁፍነት ወደ ተራ የቡና ወሬነት ያደላሉ።

ጥናታዊ ፅሁፍህ ላይ ያቀረብካቸውን መረጃዎች እንዴት እንዳሰባሰብካቸው የተገለፀ ነገር የለም? ብሎ ኤርሚያስ ለጠየቀህ ጥያቄም መልሱን «ኤርሚያስ ሆይ!» ብለህ በጀመርከው የመልስ ፅሁፍም ፕሮጀክተር ላይ ለሰወች እንዳሳየሃቸው ነገርከን እንጅ ለኛ ልታሳየን ስላልቻለክ ዳታወ ቪዲዮ ወይም አኒሜሽን ሊሆን ይችላል ብየ አልፍሃለሁ፡፡

ጥናታዊ ፅሁፍህን አስመልክቶ ኤርሚያስ ለገሰ ለጠየቀህያቀረብከውን መረጃዎችህን እንዴት እንዳሰባሰብካቸው፤ በጥናታዊ ጵሁፍህ ላይ በአሁን ሰአት ያለውን የኢትየጵያ ሙስሊሞች ” ኢትዬጲያዊነት የተላበሰ፣ ሰላማዊና ፍትሐዊ ጥያቄ” ማንሳት እነዳልፈለክ፤ ለምን አሁን?፣ ምን አዲስ ነገር ተገኝቶ ነው ይሄን ጥያቄ ይዘህ ብቅ እንዳለክ የጠየቀህ ቢሆንም ጽሑፉ ነሐሴ 25 ቀን 1999 ዓም አሜሪካ እንደቀረበ የሚገልፅ ነበር ዳሩ ግን «አክራሪ እስልምና የኢትዮጵያ ክርስትና አስቸጋሪው ፈተና Published on Feb 20, 2015 Deacon Daniel Kibret https://www.youtube.com/watch?v=4u6ItFJeG4A »

50ኛው ደቂቃ 39ኛ ሰከንድ ላይ በ1987 ዓም ከተደረገው ሀገርአቀፍ ቆጠራ በሗላ የአምና በ2006ጥናትህን የኢቶጵያን ህዝብ በክልሎች ከፍለህ ስታበራራ ነበር፡፡ጥናቱ የቀረበው በ1999 ዓም፣ አንተ ጥያቄውን ያነሣኸው ደግሞ በ2007 ነው ብለህ ኤርማስን መቸ እነደቀረበ ሳያጣራ ብለህ ከመወንጀልህ በፊት ከላይ በተጠቀሰው ደቂቃና ሰከንድ እንደገለፅከው 2006ን አምና እያለክ ኤየገለፅክ «ስሜ ነው እንጂ እኔኮ ነቢይ አይደለሁም» እያለክ በማፌዝ ኤርሚያስን ለመዝለፍና ለመወንጀል ሞከረሃል ለመሆኑ የትኛውን 2006 ይሆን ፅሁፍህ ላይ «አምና2006» ብለህ የምትጠራው የፈረንጆችን እንዳልል «በ1987 ዓም ከተደረገው ሀገርአቀፍ ቆጠራ » ብለህ ከጠራህ በኋላ ስለሆነ 2006 ዓ.ምን ያበራራሀው ይሄንንም እዛው ፐሮጀክተሩ ላይ ይሆን ምናገኘው እንደዛ ከሆነ የፕሮጀክተሩ ማሳያ ብትር በተረ-ሙሴ መሆነ አለበት።

አንተና የኢህአዴግ ባለስልጣናት ለኢትዮጵያ ሙስሊም ያላችሁን ትልቅ ጥላቻ በድጋሚ ለመገንዘብ ችያለሁ አንተ (በ2000 ዓም ጥናቱን ካቀረብኩት በኋላ ነው ‹ሽመልስ ከማል ሠራው› ያልከው ጥናት ለመንግሥት የቀረበው፡፡ ያ ጥናት ለመንግሥት አካላት ሳይለዋወጥ መቅረቡን በወፍ በረር እናውቅ ነበር፡፡ ስለዚህም የተከተለ ከቀደመ ይወስዳል እንጂ የቀደመ ከተከተለ አይወስድምና ‹ቃላት ሳይቀየሩ የቀረበው› እኔ ያቀረብኩት ጽሑፍ እንጂ በእናንተ ስብሰባ ላይ የቀረበው ጽሑፍ ወደ እኔ መጥቶ ሊሆን አይችልም ) ስትለን
ኤርሚያስ ደሞ በጥናቱ ውስጥ ያሉትን መረጃዎች እንደወረደ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማው በ2001 አም ከሽመልስ ከማል ነበር ፤ከግማሽ በላይ የአንተ ዶክመንት አባሪ እነደረገበት፤ ከአራት ሚሊዬን በላይ በሆኑ የኢህአዴግ አባላት ውይይት እንደረገበት እነደተቃወሙት ይገልፅልናል።

በስተመጨረሻ ወደ ዋናው ቁም ነገር ስመጣ ግን አነተም ቀደምክ ኢህአዴግ የሁለታችሁም ጥናታዊ ፅሁፍ ተብሎ የቀረበው ከጭፍን የሙስሊም ጥላቻ የመነጨና ኢስላምን የማጥፋት ድብቅ አጀንዳውን ከነማን ጋር አሲሮ የተነሳ ፤በአክራሪነት ስም ሆን ተብሎ ክርስቲያንና ሙስሊሙን ለማጋጨት የታቀደ መሆኑና የሙስሊሙና እርስቲያኑ አንድ መሆን እነደእግር እሳት የሚያቃጥላቸው ግለሰቦችና ድርጅቶች እነዳሉ ለማንም የተደበቀ አደለም ሆኖም እነዚህ ራሳቸውን እነደ ፀረ-አሸባሪ የሚያዩ አክራሪ ፀረ-ሰላሞች ሰላማዊ ዜጋን በማን አለብንነት የአሸባሪ ስም በመለጠፍ በየወህኒ ቤቱ በማጎርና በማሰቃየት ለታሪክ አስነዋሪ ለነገዋ ኢትዮጵያም የሚያሳፍረና የሚያወቃቅስ እየሰራችሁ የነፃነትን ትረጉም ሳታውቁ ራስን የነፃነት አረጎ ልደቴን አክብሩልኝ እያሉ መቀባጠር የረከሰ ፖለቲካ ነው።

የጥናት አቅራቢዎችም የጥላቻና እነቶፈንቶ ወሬ በመያዝ ከፀረ-ኢስላም የመንግስት ባለስልታናት ጋር ወግኖ የህዝበ ሙስሊሙን ደም መፍሰስ፣መሰቃየትና በእስር መማቀቅ ከማሴር ይልቅ ሃይማኖት በሚያዘው መልኩ በፍቅር፣በሰላም፣በመተዛዘን፣በመከባበር፣በመቻቻል ብትሰበኩ በፈጣሪ ዘንድ የተወደደና የተቀደሰ ደግ ሃሳብ ነው። ለሰው ደግ ሆናችሁ ስለደግነት ብታወሩና ብተሸልሙ ኢትዮጳ ውስጥ የምታዘጋጁት«የአመቱ ደግ ሰው» የተሰኘው አመታዊ ሽልማት በአለምአቀፍ ደረጃ አሳድጎ ሽልማቱ ቅድሚያ ለናነት በተገባችሁ ነበር።

The post ዲ/ን ዳንኤል ክብረት፣ አቶ ኤርሚያስ ለገሰና ኢህአዴግ appeared first on Zehabesha Amharic.

አቶ ቶውድሮስ አድሃኖም ሂሳቸውን ሊወጡ ነው! እናበረታታቸው እስቲ…ይዋጡ…. አይዝዎ.. (አቤ ቶኮቻው)

$
0
0

አቶ ቶውድሮስ አድሃኖም ሂሳቸውን ሊወጡ ነው! እናበረታታቸው እስቲ… ይዋጡ…. አይዝዎ…. ዋሽቻለሁ፣ ቀጥፌያለሁ…. ይበሉን መቅጠፉም መዋሸቱም ዛሬ የተጀመረ አይደለም።
ይልቅ በነካ እጅዎ… ልጅቷን ወደ ትምህርት ቤትዎ ይመልሷት፣ ትምህርቷን ጥላ የመንግስት ፕሮፖጋንዳ ሰለባ መሆኗ ነውር ነው። የህጻናት ጉልበት ብዝበዛ ይቁም! … ለመሆኑ መንግስት ለጋራ ሙለታ ህዝቦች የሚሆን በጀት እንዴት አጣ! ? የመንግስት ዋና ሃላፊነት እኮ ልክ ማስገባት ሳይሆን ልጆችን ትምህርት ቤት ማስገባት ነው!

እነሆ አቶ ቴውድሮስ… የ ሃያ ሚሊዮኑን ጉዳይ በበሪቱ ላይ ሲያሳብቡ!

11015071_902189619825781_2601891041881579942_n

11015071_902189619825781_2601891041881579942_n

The post አቶ ቶውድሮስ አድሃኖም ሂሳቸውን ሊወጡ ነው! እናበረታታቸው እስቲ… ይዋጡ…. አይዝዎ.. (አቤ ቶኮቻው) appeared first on Zehabesha Amharic.

አዲሱ የወያኔ ዘመቻ!

$
0
0

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

Amsaluበመጽሐፈ ገጽ (በፌስ ቡክ) ጓደኝነት ጥቂት የማልላቸው የኢትዮጵያዊነትን የሀገር የወገን የማንነት የቅርስ ተቆርቋሪነትን ስሜት የተላበሱ የሚያስቀናና የሚንቀለቀል ወኔ የተሞሉ እኅቶች ወንድሞች የመጽሐፈ ገጽ ጓደኝነት እየጠየቁኝ እየተቀበልኳቸው በተቻለኝ መጠንም እያበረታታሁ በጉድኝነታችንን እስከአሁን ቀጥለን ነበር፡፡ ለካ እነኝህ ኢትዮጵያዊነትን የተላበሱና ወኔ የተሞሉ ቁጭት የሚበላቸው እያልኩ የማወድሳቸውና የተቻለኝን ያህልም ሳበረታታቸው የነበሩ ወንድሞችና እኅቶች ወያኔዎች ያሁሉ ስሜትና ተቆርቋሪነታቸውም ጭንብል ወይም ሽፋን ኖሯል ለካ ሰሞኑን እነኝህ ሰዎች በዘመቻ በየአቅጣጫው “ከአሁን በኋላ አማራ ስለ ራሱ ብቻ ማሰብ ይኖርበታል፣ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ እያለ ስለራሱ ማሰብ ትቶ ለ80 ምናምን ብሔረሰብ ሁሉ ማሰብ ለድንበር መበላሸት አለመበላሸት ማሰብ የለበትም፣ አሁን 30 ምናምን ሚሊዬን አማራ ሕዝብ እስከ መኖሩም ለተዘነጋው በችግር በዘረኝነት በረሀብ በሥደት አለንጋ ለሚገረፈው የራሡ ቤተሰብ ብቻ ማሰብ መቻል አለበት፣ ሀገር ማንነት ምናምን እያለ የራሱን ህልውና አደጋ ላይ መጣል የለበትም” ከማለትም አልፈው ካርታ ሠርተው ጎንደር ጎጃም ወሎንና ሸዋን አካለው “መገንጠል ይኖርብናል” በማለት መገኝጠልን በማቀንቀን የምትገነጠለዋንም ሀገር “አማራ፣ ቤተ አማራ፣ አቢሲኒያ፣ ኢትዮጵያ፣ ግዮን” የሚሉ ስሞችን ለምርጫ አቅርበዋል፡፡ ስለ ወደብ አገልግሎት ጥያቄ ሲመልሱም “እኛ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ሀገር ድንበር ማንነት ምንትስ የሚለውን ትተን እራሳችንን ብቻ ካሰብን በራሳችን ጉዳይ ላይ ብቻ ካተኮርን ከሌሎች ጋር ሰላም ስለምንሆን የወደብ አገልግሎትን በጎንደር በኩል ከኤርትራ ማግኘት እንችላለን” ይላሉ፡፡ አንዳንድ ወገኖችንም ይሄ ሴራ የወያኔ መሆኑን ካለማወቅና የጨነቃቸው ወገኖች ያቀረቡት ሐሳብ መስሏቸው ለመደገፍ የዳዳቸው ሁሉ ነበሩ፡፡ ለአንደኛው ምን አልኩት፡-
ወንድሜ ምን ነካህ? ምን ሆንክ? ይሄ እኮ ተሸናፊነት ነው እጅ መስጠት እኮ ነው፡፡ እስኪ አሁን አንተን ከወያኔ ምን እንደሚለይህ ንገረኝ? ኢትዮጵያን ስለተውክ እንዴት ነው እራስህን ልታድን የምትችለው? ውጊያው እኮ አማራ ኢትዮጵያን እስኪተው እስኪጥል ማንነቱን ማለትም አማራነቱን እስኪክድ ድረስ ብቻ ሳይሆን ጨርሶ ዘሩ እስኪጠፋ ድረስ እኮ ነው፡፡ ምን ነው ሲበዛ የዋህ ሆንክብኝ? የትኛውንስ ክፍል ነው የምትገነጥለው? ወያኔ ከጎንደር ከጎጃም ከወሎ ውስጥ አገዎችን ቅማንቶችንና ሌሎች ወገኖችን እያነሣሣ ምን እንዲሉ እያደረገ እንደሆነ አታውቅም? ይሄ አስተሳሰብ የመጨረሻዎቹ የደናቁርቱ የድንቁርና የድንቁርና ብቻም ሳይሆን የጠላትነት አስተሳሰብ ነው የኢትዮጵያ ጠላት አስተሳሰብ፡፡ አንድነት ወይም የኢትዮጵያ ህልውና በምንም ተአምር ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም፡፡ ለሱም እንደ እናት አባቶቻችን ሁሉ የማንከፍለው የመሥዋዕተነት ዓይነት ሊኖር አይገባም፡፡ የኢትዮጵያ ነፍስ ያለው በአንድነቷ ውስጥ ነው አንድነቷ ከፈረሰ በድን ትሆናለች ትሞታለች፡፡ ኢትዮጵያ ከሞተች በኋላ ደናቁርቱና የጠላት ቅጥረኞች ይመስላቸዋል እንጅ በየትኛውም የፈራረሰ አካሏ ላይ ሰው መኖር የሚችልበት ዕድልና ሁኔታ አይኖርም፡፡ ለኢትዮጵያ መፈራረስ ተባባሪ የሆነ ሰው የሚጠየቀው በታሪክ ፊት ብቻ ሳይሆን በቅዱስ ቃሉ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ እያለ ከ70 ጊዜያት በላይ በክብር በፍቅር በሞገስ በሚጠራት በእግዚአብሔር ፊትም ነው፡፡ ለኢትዮጵያ (ለእግዚአብሔር ሀገር) ጠላት መሆን ያስኮንናልና ተጠንቀቅ፡፡ አልኩት፡፡
ብቻ ምን አለፋቹህ በመጽሐፈ ገጽ ሰሞኑን እያያቹህት እንዳላቹህት ይህ ዘመቻ እንደኛ ናቸው ብለን እናስባቸው በነበሩ አሁን ግን ባልጠበቅነው መንገድ በራሳቸው ጊዜ ማንነታቸውን በገለጡት በወያኔ ካድሬዎች በሰፊው የተያዘ ዘመቻ ሆኗልና እንዳትሳሳቱ እንዳትሰናከሉ ማስጠንቀቅ እወዳለሁ፡፡ ይህ ዘዴ ወያኔ እስከዛሬ የያዘው የአማራን ብሔራዊና የባለአደራነት ስሜት ለማጥፋት የደከመው ድካም በፈለገው ፍጥነትና መጠን ውጤት እንዳላመጣለትና ብዙም ውጤታማ እንደማያደርገው ካወቀ በኋላ አዲስ የቀየሰው ስልት ነው፡፡ ነገር ግን በእኔ እምነት ይሄ የወያኔ አዲሱ የኢትዮጵያዊነትንና የባለአደራነትን ስሜት ከአማራ የማጥፋትና ሀገሪቱን ባለቤት ባለአደራ ተቆርቋሪ የማሳጣት እኩይና ሰይጣናዊ ዘመቻ እንደቀደመውና ሲሠራበት እንደቆየው ዘመቻው ሁሉ ይከሽፋል እንጅ ይሠራለታል ብየ አላስብም፡፡ ወያኔ የኢትዮጵያዊነትን ስሜት ከሌሎቹ ብሔረሰቦች በተሳካ መልኩ አጥፍቻለሁ ብሎ ያስባል የቀረኝና ያቃተኝ አማራ ብቻ ነው ብሎ ያስባል፡፡ መስሎት እንጅ የኢትዮጵያዊነትን ስሜት ከኢትዮጵያዊያን አጠፋለሁ ማለት ቅዠት ነው፡፡ ከደሙ ጋር ተቀላቅሎ ያለ ነውና፡፡

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

The post አዲሱ የወያኔ ዘመቻ! appeared first on Zehabesha Amharic.


አንድነት ፓርቲና ውለታው –ከሃቅ ማህደር። –ከሥርጉተ ሥላሴ

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 08.03.2015 /ሲዊዘርላንድ ዙሪክ/

Womansday

የ2015 ዓለምዓቀፍ ሴቶችን ቀን እኔ በግሌ ዕለቱን ያሰብኩትን መጠነ ሰፊ አቅም ዬነበረውን በወንበዴው በወያኔ ትእቢት በቀላጤ የፈረሰውን የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲን፤ እስረኛዋን እናት ሀገሬን፤ እስረኛ እህትና ወንድሞቼን፤ በራህብ – በመፈናቀል ሰቆቃ ላይ ያሉ ወገኖቼን አስቤ ነበር። አንድነት ፓርቲ ዬብሄራዊነት ምንጩ ከቅንጅት መንፈስ የተነሳ ብቻ ሳይሆን የሴቶችን አቅም ያዳመጠ በኽረ ፓርቲ በመሆኑም ጭምር ነው።

አንድነት ለእኛ  ትውልድ፤ እኛ ለተፈጠርንበት ትውልድ፤ የመጀመሪያዋን ሴት የፓርቲ መሪ ክብርት ዳኛ ብርቱካን ሜዴቅሳን በብሄራዊ ደረጃ እንድትመራ፤ እንድታስተባብር የፈቀደ ብቸኛው ፓርቲ ነው። አንጋፋነቱን ሆነ የትውልድ ልዑቅ ፓርቲ መሆኑን ማመሳከር የሚችለው ሃቅም ይኼው ነው። የሴቶችን አቅም ፍሰት በዚህ ዙሪያ ቆጥቦልናል።  ለአንድነት ፓርቲ ስለ ሴቶች የማድረግ ሙሉ አቅምና ሥጦታ ቅስቀሳ አያስፈልገውም ነበር። ዛሬ አንድነት የለም። አፍርሰዉታል። ንደውታል፤ ዘርፈውታል፤ መንፈሱን ቀምተውታል፤ ብቃቱን አራቁተውታል። እንዲህ እንደ ሚታየው ፎቶ ዕንባችን ከውስጥ ሞልቶ ውጩንም አርሶታል። የምር መራራ ቀን ነበር ….

እኔ የአንድነት መፍረስ የሰማሁ ዕለት ሰውነቴ ተቆረሰ፤ መንፈሴ ተናዳ፤ ህሊናዬ ቆሰለ። አንድ ብሄራዊ ፓርቲ ፈቃድ ተሰጥቶት ከተደራጀ በኋላ፤ ጊዜውን፣ አቅሙን፤ ጉልበቱን አፍስሶ ከሁሉ በላይ መሪዎቹን በተለያዬ ጊዜ ለካቴና – ለስለት፤ ለድብደባ – ለመደፈር ሰውቶ እንዲህ መስዋዕትነቱን ሁሉ መና በማደረግ ሲፈርስ ማዬት ከዚህ የበለጠ የሃዘን ቀን አልነበረም ለእኔ። ሁላችሁም እንደምታውቁት 90 ሚሊዮን ህዝብ ልሰደድ ቢል አይችልም፤ ጫካ ልግባ ቢልም እንዲሁ፤ ስለሆነም ነበር አንድነት አቅሙ የፈቀደውን የህዝብ አንጡራ ፍላጎት መርሁ በማድረግ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ከባርነት ለመላቀቅ፤ ቀጥሎም ዴሞክራሲን ለማስፈን ትግል ማደረግ ግድ ይለው ስለነበር አብዝቶ መስዋዕትነቱን የተቀበለ።

ሰላማዊ በሆነ መንገድ የታገሉ መሪዎቹ ሲታሰሩበት አዲስ በመምረጥ፤ ሲደበደቡበት በመንፈስ ከጎናቸው በመሆን፤ ሲሳደዱበት በማበረታታ፤ በሆደ ሰፊነት የአመራር ተካታታይነቱ በወያኔ ጣልቃ ገብነት ባልተቋረጠ ሁኔታ ቢደፈርስበትም ሳይታክት እርግብን አምኖ፣ ዘንባባን ተደግፎ ብዙ በጣም ብዙ ጥረት አድርጓል። ይቻላል – ይቻላል ይቻላል እያለ …. ጣረ ታገለ ታተረ …. ግን …. ሞት ተበዬነበት።

ከሁሉ በላይ ለእኔ መንፈስ እጅግ ቅርብ የሆነው የአንድነት ጉዳይ የኢትዮጵያ ሴቶችን ልዩ ብልህ አቅም ዕውቅና የሰጠ ብቸኛው ብሄራዊ ፓርቲ መሆኑ ነበር። 40 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ፓርቲዎች ሁሉ ያለደረጉትን ነገር ነበር አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ደፍሮ ያደረገው። በሌላ በኩልም አስተውላችሁት ከሆነ የአውሮፓ ኮሚሽን ዕንባችን የተጋራው ወላዊ የነፃነት ትግል ብርቱ ዕውቅና ዓርማው ሴት ነበረች። ክብርት ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ። ጋዜጠኛ ርዕዮትም የአንድነት ፓርቲ የምክር ቤት አባል ነበረች። ምንም እንኳን ከተገለሉት ውስጥ የነበረች ብትሆንም መነሻ ቤቷ አንድነት ነው። የእውነት መጨረሻው እውነት ነውና እውነተኞች ነጥረው አሁንም ጥቃት ስፈጸምባቸው ክብርት ጋዜጠኛ ርዕዮትና ሌሎች ቀደምት የአንድነት መሪዎች የተገለሉበት ሃቅ ዘመን ሰጠው።

40 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ፓርቲዎች ወይንም 23 ዓመት ዕድሜ ያላቸው የጎሳ ድርጅቶች አንድ ዓለም ዓቀፍ ዕውቅና ያላት ሴት ወይንም መሪ ወይንም ጋዜጠኛ አላፈሩም። አንድነት ግን አለው። በእኛ የሴቶች ታሪክ ውስጥ ልዩ ማህደረ – ዝክረ ነው። የአንድነት ሚስጢር ያለው ከዚህ ላይ ነው። አንድነት የመጀመሪያ የህይወት ትምህርት ቤት የሆነችውን እናት – ሴት – እህት – ሚስት – ጓደኛን፤ ጸጋ አልተላለፈም። ይህን ሃቅ የደፈረ- ያስተማረ – በተግባር አንድነት ብቻ ነው። ሴት እኔን ትምራኝ ብሎ መፍቀድ ከውሳኔዎቹ ሁሉ እጅግ ፈታኙ ነው። ይህን ጀርመኖችም ሲዊዞችም አድርገውታል። ውጤቱንም አዬተውታል።

ስለሆነም የኢትዮጵያ ሴቶች አትኩሮት፤ አክብሮት፤ ልቅና የሰጣቸውን ፓርቲያቸውን በማንለኝበት ወያኔ በቁሙ ሲያፈርስባቸው መቆጣት አለባቸው፤ መበሳጨት አለባቸው፤ ስለምን? ብለው መንገብገብ አለባቸው፤ ጉዳያችን ነው ብለው በባለቤትነት ስሜት ፊት ለፊት ወጥተው በሰላማዊ መንገድ ተራጋጩን የወያኔ ሃርነት ትግራይን ማንፌስቶ አስፈጻሚዎች መጠዬቅ አለባቻው። ትእቢተኛውን የጎሳ ድርጅት መልስ እንዲሰጣቸው በተከታታይነት መጠዬቅ አለባቸው።

ቢያንስ የትዕቢተኛውን ትብትብ መንፈስ ክፍተት ከውስጡ መፍጠር አለባቸው። ንፋስ አብጠልጥሎ አናቱን እንዲፈርሰው ተግተው መጠዬቅ አለባቸው። በፌስ ቡክ፣ በቲተር፣ ወይ በጉጉል ወይ በግልጽ ደብዳቤ ሊሆን ይችላል። እርግጥ የብሄራዊ ነፃነት መፍጫው የምርጫው ክፍለ ጊዜ ሲያልፍ የሚኖር አዲስ የድብብቆሽ ትወና ሊኖር ይችላል። የሆነ ሆኖ ለዘለቄታ – ከባርነት ወደ ነፃነት፤ ከጭቆና ወደ ዴሞክራሲ መሸጋገር ብቻ ሳይሆን የሴቶችን የመሆን አቅም በእኩልነት እስኪሰፍን ድረስ መትጋት ግድ ይላል። የአንድ ሀገር ዴሞክራሲ መጠን የሚለካው ለሴቶች ከሚሰጠው ዕውቅና ስፋትና ጥበት ይወሰናልና።

እኛ እንዳለፍነበት ዘመን የኢትዮጵያሴቶች አቅም መባከን ወይንም ከከርሰ ምድር ውስጥ እንዳለ ሃብት አፈር ለብሶ መቅረት የለበትም። አዲሱ ትውልድ ሴቶች ከወንዶች ጋር ተወዳድረው በሴትነታቸው ሳይሆን በመጠነ ሰፊ ብቃታቸው፤ በእናታዊ ጸጋቸው፤ በድርጁው መንፈሳቸው፤ በሚስትነት ስጦታቸው፤ በመምህርነት ክህሎታቸው፤ በማህበራዊነት መክሊታቸው ማሸነፍ አለባቸው። ዘመኑንም – መምራት። የእኔ ህልምና ናፍቆት ዬአፍሪካ አንድነት ድርጅት፤ የተባባሩት መንግሥታት ድርጅት፤ የአውሮፓ ኮሚሽን አሜሪካን ጨምሮ የበርካታ ሀገሮች መሪዎች ሴቶች እንዲሆኑ ነው። ከሴቶች ውስጥ ያለውን ሚስጢር ማንም ፈላስፋ ወይንም ሳይንቲስት ተመራምሮ እስካሁን አልደረሰበትም። ለነገሩ በሴቶች የብቃት ልክ ምን የምርምር ሥራ ተሰርቶ በፍጹም ሁኔታ የተዘለለ አምክንዮ ክስተትም ነው። ሴቶች ፍቅር ናቸው። ፍቅር ደግሞ ሁሉንም ነው መሬት ….

ኢትዮጵያ ሀገራችን በነገው የሴቶች ዓለም ትደምቅ ዘንድ፤ ተጠቃሚ ትሆን ዘንድ፤ ሴቶች ዛሬን አብረው መሆን አለባቸው ነገን ለማግኘት። ግፊያው አለ፤ ግን ስልቱም ስላለ ማሸነፍ ይችላሉ – አይበገሬነት ከጠጡ፤

ሰሞናቱን ጀርመኖች በሁሉም ፓርቲዎቻቸው ጉልህ አጀንዳው በሴቶች እኩል ተሳትፎና ውጤት ግምገማ ላይ ነበሩ። ለዛውም በተመጠነ የቁጥር ተዋፆ በአኩልነት ላይ የተመሰረተ ተሰትፎ ባለበት ሀገር … እኔ ንጉሥ ዳዊት „የቤትህ ቅናት በላኝ“ እንዳለው ነበር ያደረገኝ ….

ወደ ኢትዮጵያ ጎራ ሲባል ደግሞ የትውልድ ፈርጦች የነገ ፍሬዎች „ነፃነት“ ባሉ የጣይቱ ልጆች ባለፈው ዓመት ምን እንደደረሳባቸው ይታወቃል። ዱላ፤ እስር …. መደፈረ ….  የዓለም ሴቶች የ2014 ቀናቸውን በፍሰሃና በደስታ ሲያሳልፉ የኢትዮጵያ ሴቶች ደግሞ በወያኔ ርግጫና ፍጥጫ ….

የብሎገር ጸሐፍት ታታሪዎች እንዲሁም የድምጻችን ይሰማ የካሜራ ታታሪ ሴት እህታችንም ጨምሮ ሊበረታቱ፣ ሊደነቁ፣ ሊደገፉ፣ ሊሸለሙ ሲገባቸው፤ በተመሳሳይ ሁኔታ የደረሰባቸው ፍዳና መከራ ነው። በጥቅሉ ዕለቱን ኢትዮጵያ ላይ ሲታሰብ የወያኔ ሃርነት ትግራይ ዘር ተከል ጨለማዊ አገዛዝ ተወግዶ፤ በልቡ የታበዬው ገዢ ፓርቲ ተወግዶ፤ አቅማችን – ችሎታችን፤ ሊደመጥ የሚችልበት ሥርዓትን መናፈቅ፤ ለናፍቆት „በቃንን“ ማስታጠቅ አንገብጋቢው መስመራችን ሊሆን ይገባል።

በተረፈ „በድምጻችን ይሰማ“ ያለው ጉልበታም እንቅስቃሴ ሆነ ጉልህ ድንቅ የሴቶች ተሳትፎ ለዛላቂ የነፃነት ትግል ከሚደረገው ጋር አቀናጅቶ የሴቶችን ሰማያዊ ሚስጢር ኢትዮጵያ ላይ ጥቅም ላይ ለመዋል – እንትጋ። እግዚአብሄር አምላክ ለአፈራችን ያብቃን አሜን! እግዚአብሄር ይስጥልኝ ዘሃበሻ ማህበራዊ ድህረ ገጽ። ለሰጣችሁኝ የማያልቅ ጣፋጭ የብዕር እኩልነት ነፃነት ምልክቴ ናችሁ – ኑሩልኝ። አድማጪዎቼም – ኑሩልኝ!

 

ሴት የአቅም ፈላስፋ ናት!

ዓለም ዓቀፍ ሴቶች ቀን የካቲት 29 ለዘለዓለም ይኑር! ….

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

 

The post አንድነት ፓርቲና ውለታው – ከሃቅ ማህደር። – ከሥርጉተ ሥላሴ appeared first on Zehabesha Amharic.

(ዜና ፎቶ) መርካቶ አካባቢ ያሉ ወጣቶች አዛውንቶችን እና የአእምሮ ህመም ያለባቸው የጎዳና ተዳዳሪዎችን ገላቸውን ሲያጥቡና ጸጉራቸውን ሲላጩ ዋሉ

$
0
0

የዘ-ሐበሻ ወዳጅ ከአዲስ አበባ የላከው ፎቶ ነው:: ጸሐፊው የመንግስት ባለስልጣናት ቀይ ቀረባት አስረው በአደባባይ ሲዋሹ ወገን ለወገኑ እንዲህ ያደርጋል ሲሉ ፎቶውን ልከውልናል:: ዛሬ ከጠዋቱ 4 ሰዓት አካባቢ አዲስ አበባ አንዋር መስጊድ አካባቢ የሚገኘው ቶታል አጠገብ ወጣቶች በአካባቢው የአእምሮ ህመም ያለባቸውንና በእድሜ የገፉ የጎዳና ተዳዳሪዎችን ገላቸውን ሲያጥቡ እና ጸጉራቸውን ሲላጩላቸው ውለዋል:: ይህን ደስ የሚል በጎ ተግባር ለዘ-ሐበሻ አንባቢዎች እንዲደርስ ፎቶውን የላከልን ወዳጃችን “መንግስት ከዚህ ምን ይማራል?” ሲል ይጠይቃል::
addis ababa

merkato addis ababa copy

The post (ዜና ፎቶ) መርካቶ አካባቢ ያሉ ወጣቶች አዛውንቶችን እና የአእምሮ ህመም ያለባቸው የጎዳና ተዳዳሪዎችን ገላቸውን ሲያጥቡና ጸጉራቸውን ሲላጩ ዋሉ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢሕአዴግኣዊ ዴሞክራሲ እና ሊብራሊዝም – ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ

$
0
0

አዲስ አድማስ ጋዜጣ ቅፅ 15 ቁጥር 789፣ የካቲት 28 ቀን 2007 ዓ.ም)

መግቢያ

ኢሕአዴግ፣ የዐፄውን ሥርዐት ርዝራዥና የደርግን አስከፊ ሥርዐት አፈራርሼ አገሪቱን በተሻለ የዴሞክራሲ ጎዳና እየመራኹ ነው በማለት ያለመታከት እያበሠረና እየወተወተ ይገኛል። ካለፈው ሥርዐት አላቅቄኣችኋለኹ የሚለው የራሱ እውነታ ቢኖረውም፣ በአንጻሩ ግን ኢሕአዴግ ራሱ የሚያበጅልን ዐዲስ ቀንበር መልክ አውጥቶ ዐደባባይ ወጥቶ መታየቱ አልቀረም፡፡ ያረጀውን አገዛዝ በዐዲስ አሠራር ከሚጭንብን ከዚኽ ዐይነቱ ቀንበር መላቀቅ የኢሕአዴግ ችግር ሳይኾን፣ የእኛ የአገሪቱ ዜጎች ችግር እና የቤት ሥራ መኾኑን መረዳት ይኖርብናል።
የዚኽ መጣጥፍ ቀዳሚ ዓላማ÷ ከኹለት ዐሥርት ዓመታት በላይ የቆየው የኢሕአዴግ አገዛዝ ከዴሞክራሲ፣ ከዜጎች ነጻነትና መብት አኳያ ምን ዐይነት መንገድ ይዞ እየኼደ እንደኾነና ኢሕአዴግ በጥቂቱም ቢኾን ከጀመረው የዴሞክራሲ መንገድ ስቶ የኋላ ኋላ ራሱን ወደ ኢ-ዴሞክራሲ አገዛዝ እንደምን እንደቀለበሰ በተወሰነ መልኩ ለማሳየት ነው። መጣጥፉ በሦስት ንኡሳን ርእሶች የተከፈለ ነው፡፡ በክፍል አንድ፣ የዴሞክራሲ እና የሊብራሊዝም ፅንሰ ሐሳቦችን ከአገራችን ኹኔታ ጋራ በማያያዝ የመንደርደሪያ ሐሳብ እሰጣለኹ። በክፍል ኹለት፣ በሰው ልጆች የቅርብ ታሪክ ውስጥ ዴሞክራሲ እና ነጻነት ለመጎናጸፍ ይበጃሉ የሚባሉት ተቋማት÷ ለምሳሌ፣ እንደ ፓርላማ፣ የፍትሕና የሚዲያ፣ የመድበለ ፓርቲና የምርጫ ሥርዐት እንዲኹም ሲቪል ማኅበራትን ኢሕአዴግ እንደምን መንፈሳቸውን ቀይሮ የራሱ የፖለቲካ መገልገያ እንዳደረጋቸው፤ የምርጫ ሥርዐቱን በምሳሌነት በማንሣት ሐተታና ትችቴን አቀርባለኹ። በክፍል ሦስት፣ በአገራችን የፖለቲካ ሕይወት ውስጥ የሚገኘውን አፍራሽ የኾነ የፍትሕ አቀራረብ በማሳየትና በመጨረሻም፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ዐጭር ማስታወሻ በማኖር መጣጥፉን እቋጫለኹ።
dr dagnachew Assefa
፩. የዴሞክራሲ እና የሊበራሊዝም ነገር

እንደ ዕውቁ የሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ምሁር ሳሙኤል ፒ. ሃንቲንግተን እይታ፣ በቅርብ የሰው ልጅ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ በተለያዩ ጊዜዎች ሦስት የዴሞክራሲ ሞገዶች ተከሥተዋል። ከፍጹማዊ አገዛዝ ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዐት የተደረጉትን ሽግግሮች ምሁሩ በሞገድ አምሳል ያቀርቧቸዋል። እንደእርሳቸው ትረካ፣ የመጀመሪያው ሞገድ ከፈረንሳይና ከአሜሪካ ዐብዮት በኋላ በ19ኛው ምእት መባቻ የተነሣው ሲኾን ተከታዩ ደግሞ ከኹለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በብዙ አገሮች ውስጥ የታየው ነው፤ ሦስተኛው ደግሞ ከ1974 እስከ 1990 (እ. አ. አ.) ሠላሳ ያኽል አገሮች ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዐት የተሸጋገሩበት ነው፤ ምሁሩ ይህን የሽግግር ወቅት “ሦስተኛው የዴሞክራሲ ሞገድ” የሚል ስያሜ ሰጥተውታል።
ከሦስተኛው ሞገድ በኋላ ግን ሒደቱ የዴሞክራሲ ልምላሜን እያጠወለገ፣ በአንዳንድ አገሮች ውስጥ ወደ ኋላ ይቀለበስ ጀምሯል፡፡ ከእኒኽ አገሮች መካከል ኢትዮጵያ አንድዋ ናት። የአገሮቹ መንግሥታት ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዐት ግንባታ ገብተናል ብለው ሲያውጁ፣ ነጻነት እና የመብት ጥያቄዎች ቀዳሚ ቦታ ይይዛሉ ተብሎ ተገምቶ ነበር። ኾኖም ግን፣ እነዚህ መንግሥታት የዴሞክራሲን መዋቅር ሌጣውን ተቀበሉ እንጂ በባሕርያዊነት አብሮት የሚሔደውን የሊብራሊዝም ጎዳና ስላልተከተሉ፣ በአሉበት እየረገጡ ወደፊት መራመድ ተስኗቸዋል።

በዚህ ዙሪያ ወሳኝ ጥናቶችን ያደረጉ ሰዎች እንደሚናገሩት፣ የዴሞክራሲ እና የሊብራሊዝም ፖለቲካዊ መርሕ ከፍልስፍና አንጻር ሲታዩ አንድነትም ልዩነትም አላቸው። የሰው ልጅ ምሉዕ የኾነ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ፍትሐዊ ነጻነት ይኖረው ዘንድ የዴሞክራሲ እና የሊብራሊዝም መስተጋብር የግድ ይላል። ዴሞክራሲ የሚለው ቃል በዋናነት ሕዝብን ከዓምባገነናዊ ኀይል የሚከላከል ጋሻ (Demo-protection) ሲኾን፣ ሊብራሊዝም ደግሞ የሕዝብ ሉዓላዊነት (Demo-power) ነው። ዐዲሶቹ “ዴሞክራሲያዊ” መንግሥታት በተወሰነ ደረጃ የዴሞክራሲን አንዳንድ ፈለጎች ለመከተል ባይቸገሩም፣ የሊብራል ጥሪዎችን ማድመጥ ግን በእጅጉ ተስኗቸዋል።

ምናልባት፣ በዴሞክራሲ እና በሊብራሊዝም መሀል እንዴት ወይም ምን ዓይነት ልዩነት ሊኖር ይችላል ብለው የሚጠይቁ ሰዎች ስለሚኖሩ በዚኽ ዙሪያ ጥቂት ብለን ማለፉ ተገቢ ነው። አንደኛ፣ ዴሞክራሲ የሚያተኩረው በሥልጣን ክፍፍል፣ በየጊዜው በሚደረጉ ምርጫዎች፣ በብዙኃን መገናኛ፣ በመድበለ ፓርቲ፣ በሲቪል ማኅበራት… ወዘተ ተቋማዊ አያያዝና አሠራር ላይ ነው። በአንጻሩ ሊብራሊዝም በሕግ የበላይነት፣ በመሠረታዊ የሰው ልጆች ነጻነትና መብት ላይ ያተኩራል።

ኹለተኛ፣ ዴሞክራሲ የመንግሥት ሥልጣን በሚያዝበት መዋቅር ላይ ሲያተኩር፣ ሊብራሊዝም ደግሞ የሥልጣን ወንዝ ከገደቡ ወጥቶ ዜጎችን እንዳያጥለቀልቅ ለመከላከል፣ በምን መንገድ እየተቀየሰና እየተገራ መሔድ እንዳለበትና እንደሚገባው ይደነግጋል። ይኸውም ዴሞክራሲ ተሳትፎ ላይ ሲያተኩር ሊብራሊዝም ደግሞ ተጠያቂነት ላይ ያተኩራል። በአንዲት አገር መልካም የነጻነትና የፍትሕ ሕይወት መንገድ ተይዟል የሚባለው፣ ዴሞክራሲ የሚጠይቀው ሕዝባዊ ተሳትፎና ሊብራሊዝም የሚሻው መንግሥታዊ ተጠያቂነት በአንድነት ተባብረው ሲገኙ ነው።
በፅንሰ ሐሳብ ደረጃ የዴሞክራሲ እና የሊበራሊዝም የአጽንዖት ልዩነት እንደተጠበቀ ኾኖ፣ ወደ ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ኹኔታ ስንመጣ፣ ሥርዐቱ የኹለቱንም መሠረታዊ ጥሪዎች ማስተናገድ የተሣነው ኾኖ እናገኘዋለን። የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከደርግ በኋላ፣ በተወሰነ መልኩ የዴሞክራሲ ጭላንጭል ቢያገኝም፣ ሕገ መንግሥቱ እንደሚደነግገው የሥልጣን ባለቤትነትን አልተጎናጸፈም። ይህን ለማለት የሚያስደፍረው፣ የአገራችንን ፖለቲካ ከሕዝባዊ ተሳትፎና ከመንግሥታዊ ተጠያቂነት አንጻር ስንመለከተው ትልቅ ጉድለት በመኖሩ ነው፡፡

(፩) ሕዝባዊ ተሳትፎ፦

ዜጎች በሕይወታቸው፣ በንብረታቸው፣ በማኅበረሰባዊ ኹኔታዎቻቸው ወሳኝ በኾኑ ጉዳዮች ላይ የምክክርና የውሳኔዎች አካል ባልኾኑበት ሥርዐትና አሠራር ውስጥ የዴሞክራሲ መሠረታዊ ጥሪ የኾነው ሕዝባዊ ተሳትፎ አልተወለደም ማለት ነው። ለኢሕአዴግ ግን ተሳትፎ ማለት (ሀ)አስቀድሞ የወሰነውን ነገር ሥልጠና በሚል ፈሊጥ ወደ ሕዝብ ማውረድ፣ (ለ)ባለድርሻ በሚል ፈሊጥ የራሱን ወኪሎች መርጦ ውሳኔዎች በተሳትፎ የተገኙ ማስመሰል ነው። ለሐቀኛ ተሳትፎ ግን የንግግር ነጻነት እና የመሰብሰብ ነጻነት ያስፈልጋል። መንግሥት እና ዜጎች በእኩል ደረጃ መወያየታቸው ቀርቶ፣ መንግሥት አቀባይ ሕዝብ ደግሞ ተቀባይ ኾነዋል።

(፪) ተጠያቂነት፦

መረጃ ከመንግሥት ወደ ሕዝብ የማይወርድበት አገር ውስጥ የተጠያቂነትን ሥርዐት ማሟላት በእጅጉ አስቸጋሪ ይኾናል። ሥርዐቱን ለማሟላት ከመንግሥት ቁጥጥር ውጭ የኾነ ሚዲያ ይኖር ዘንድ ግድ ይላል። ዜጎች መረጃ የሚያገኙበት መንገድ እስከሌላቸው ድረስ መንግሥትን ተጠያቂ ሊያደርጉባቸው የሚችሉባቸው መንገዶች ኹሉ ይዘጋሉ።
አንዳንድ የፖለቲካ ምሁራን፣ ዴሞክራሲ ለማበብ ረዘም ያለ ጊዜ ይጠይቃል፤ በመኾኑም ኢሕአዴግን የበለጸገ ዴሞክራሲ አላመጣም ብሎ መተቸት አግባብነት የለውም፤ የሚል መከላከያ ያቀርባሉ። የአፍሪቃ ዴሞክራሲ ገና ለጋ በመኾኑ ለመቶዎች ዓመታት ከቆየው ምዕራባዊ ዴሞክራሲ ጋራ ሊነጻጸር አይገባም፤ ሲሉም ይሞግታሉ። ለዚኽ ዓይነቱ አስተያየት ተገቢ መልስ ሰጥተዋል ብለን የምናምነው የ20ኛው ምእት ትልቁ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ጂዮቫኒ ሳርቶሪ (Giovanni Sartori) ናቸው። በእርሳቸው አመላለስ፣ ዴሞክራሲ የተለያዩ ክፍሎች ያሉት መዋቅር እንጂ አንድ ወጥ ባለመኾኑ፣ አንድ መንግሥት ቢያንስ የዜጎችን የንግግር፣ የመሰብሰብና ሐሳብን የመግለጽ ነጻነትን ለማክበር ምን ያኽል ጊዜ ያስፈልገዋል? ጋዜጠኛን ላለማሰር፣ የፖለቲካ ስብሰባዎችንና ሰላማዊ ሰልፎችን ላለመከልከል ሥርዐቱ ስንት ዘመን መቆየት ይኖርበታል?
በእኔ በኩል በዴሞክራሲ ፍላጎትና በገዢዎች ፍላጎት መሀል የተዘረጋው ቅራኔ እንደተጠበቀ ኾኖ፣ ከዚህ ቀደም ለማሳየት እንደሞከርኹት፣ የአገራችን የዴሞክራሲ ሥርዐት ግንባታ ለችግር የተጋለጠበት አንዱ ምክንያት፣ አውሮጳውያን በዘመነ አብርሆ ለመቶ ዓመታት ያኽል እንደአደረጉት፣ በሊብራሊዝም ባህል ላይ የተመሠረተ የሐሳብና አመለካከትን የመግለጽ ነጻነት፣ የኅትመት ነጻነት፣ ሃይማኖታዊ መቻቻልና በጥቅሉ በመሠረታዊ የሰው ልጆች የነጻነት ጥያቄዎች ላይ አስቀድመን ብርቱ ሥራ ባለመሥራታችን ነው።

፪. ዐዲሶቹ የኢ-ዴሞክራሲያዊ ኀይሎች ሥርዐተ ተቋማት

በዚህ ርእስ ሥር በከፊል የማቀርበው ሐሳብ በዋናነት የተመረኮዘው፣ በቅርቡ የጀርመኑ የፖለቲካ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር አንድሪያስ ሺድለር (Andreas Schedler) በ2009 (እ. አ. አ.) በዴሞክራሲ ስያሜ ስለሚንቀሳቀሱት ዐዲስ መንግሥታት በአጠኑት ጥናት ላይ ነው።

ቀደም ባለው ክፍል ለማሳየት እንደሞከርኹት፣ ፕሮፌሰር ሳሙኤል ፒ. ሃንቲንግተን “ሦስተኛው የዴሞክራሲ ሞገድ” ወደፊት መገስገሡን ትቶ፣ የቀኝ-ኋላ ዙር መንገድ መከተሉን መግለጻቸውን አውስቻለኹ። ሌሎች ጸሐፍትም፣ ከዚኹ የገለጻ መንፈስ ጋራ በሚሔድ መልኩ፣ ይህን ፕሮፌሰሩ ‘ቅልበሳ’ ያሉትን ፅንሰ ሐሳብ፣ አንዴ ‘ኢ-ሊብራል ዴሞክራሲ’፣ አንዳንዴ ‘ኦተሪቴሪያን ዴሞክራሲ’ የሚሉ ስያሜዎች እየሰጡ ለመግለጽ ሞክረዋል። ፅንሰ ሐሳቡ በተለያዩ ስያሜዎች ቢገለጽም፣ በዋና ጭብጣቸው፣ የሥርዐቶቹን ‘ኢ-ዴሞክራሲያዊ’ ባሕርይ የሚያሳዩ መኾኑ ላይ ግን ሙሉ ስምምነትና አንድነት አላቸው።የዴሞክራሲ ሞገድ ውስጥ የተፈጠሩት ዐዲስ ሥርዓቶች፣ በውጣኔአቸው የነጻነትና የመብት ፍንጣቂ ቢታይባቸውም፣ ከሰብአዊ ነጻነት አኳያ ሲመዘኑ ግን የተመናመነ የተሰፋ መንገድ ላይ እንዳሉ መረዳት አዳጋች አይኾንም።

“ፍጹማዊ የሥልጣን አገዛዝ” ወይም ደግሞ “የጭቆና አገዛዝ” በሚል ቀደም ብሎ የሚታወቀው ስያሜ በዐዲሶቹ ሥርዐቶች ዐውድ ውስጥ “ዴሞክራሲያዊ” የሚል ቅጽል ተለጥፎለት እናገኘዋለን። እዚኽ ላይ ማንሣት የሚገባን መሠረታዊ ጥያቄ፣ “ዴሞክራሲያዊ” የሚለው ቃል ከእኒኽ ሥርዓቶች ስያሜ ጋራ ለምን አብሮ ተያይዞ ይቀርባል? የሚል መኾን ይኖርበታል። ይህን ጥያቄ የምናነሣበት ዋነኛ ምክንያት በቀደመው ዓምባገነናዊ አገዛዝ (Dictatorship) እና በዛሬው ጠቅላይ አገዛዝ (Authoritarianism) መካከል መሠረታዊ ዝምድናና ልዩነት ይኖር እንደኾን መፈተሽ ስላለብን ነው።

ፍተሻው በቀጥታ ወደ አገራችን ተጨባጭ ኹኔታ ያመጣናል። ለመኾኑ፣ በደርግ ሥርዐትና በኢሕአዴግ ሥርዐት መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው? ደርግን “ዲክቴተርሺፕ”፣ ኢሕአዴግን ደግሞ “ኦተሪቴርያን” የምንላቸው ለምንድን ነው? የኹለቱ ሥርዐቶች ልዩነት ሲቀርብ፦ አንዱ ገዳይ፣ ጨፍጫፊ፣ አረመኔ ተደርጎ ይተነተናል፤ ሌላው ደግሞ፣ በወዳጆቹ ዘንድ፣ እንደ ነጻ አውጪ፣ የዴሞክራሲ አራማጅ ተደርጎ ሲቀርብ፣ በተቃዋሚዎቹ በኩል ደግሞ፣ እንደ ኢ-ዴሞክራሲያዊና ጎሰኛ ተደርገው እንደኾነ ዘወትር እንሰማለን። ኹለቱም አቀራረቦች ላይ ላዩን ሲታዩ በተወሰነ መልኩ እውነታ ቢኖራቸውም፣ በፅንሰ ሐሳብ ደረጃ ግን፣ የኹለቱን ሥርዐቶች መሠረታዊ ልዩነት በበቂ አይነግሩንም። በመኾኑም የቀድሞውንና የዐዲሱን መንግሥታዊ ሥርዐቶች ልዩነት በምንመረምርበት ጊዜ፣ ፕሮፌሰር ሺድለር የሚያቀርቡት ሐሳብ የበለጠ ጠቃሚ ኾኖ እናገኘዋለን።

ቀዳሚ የሚኾነው የኹለቱም ሥርዐቶች ተልእኮ ሥልጣንን ማካበት እና ሥልጣን ላይ መቆየት ነው። ከዚኽ አንጻር፣ ኹለቱም ሥርዐቶች ግባቸው አንድ ነው፡፡ ከግቡ ለመድረስ የሚጠቀሙባቸው መንገዶች ግን የተለያዩ ናቸው። እንደ ፕሮፌሰር ሺድለር አቀራረብ፣ የቀድሞዎቹ ዓምባገነኖች ሥልጣን ላይ ለመቆየት የሚጠቀሙባቸው ተቋማት ወትሮውንም በታሪክ ውስጥ የሰውን ልጅ ነጻነት በመፈታተን የሚታወቁትን፣ እንደ ‘የጦር ኀይል’፣ ‘ፖሊስ’፣ ‘ጸጥታ’፣ ‘ደኅንነት’፣ ‘ሲቪል ታጣቂዎች’ ናቸው። በሌላ በኩል፣ ዐዲስ የመጡት ዴሞክራሲያዊ ነን የሚሉት ሥርዐቶች ደግሞ የድሮውን የመጨቆኛ ተቋማት ትተው፣ የሰውን ነጻነትና መብት ያስከብራሉ የሚባሉትን የፍትሕ፣ የሕግ አውጪ፣ የምርጫ፣ የብዙኃን መገናኛ ተቋማትን ወዘተ… በጭቆና መሣሪያነት ይጠቀማሉ።

እዚህ ላይ ተገቢ የሚኾነው ጥያቄ፣ ለነጻነት የታሰቡ ተቋማት እንደምን ተቀልብሰው የመንግሥት መጠቀሚያ ለመኾን በቁ? የሚል ነው። በመኾኑም በዚህ ጉዳይ ላይ ትንሽ ገለጻ ከሰጠን በኋላ፣ የፍትሕ ተቋማትን፣ የብዙኃን መገናኛ ተቋማትንና የምርጫ ተቋማትን በምሳሌነት እናነሣለን።

ከኹሉ አስቀድሞ፣ ዐዲሱ ሥርዐት ሥልጣን በሚይዝበት ጊዜ የሚረከበው “ባዶ የፖለቲካ ተቋማዊ መሬት” (institutional tabularasa) አያገኝም። እንዲያውም ካለፈው ሥርዐት የቀጠሉ ርዝራዥ ተቋማት ተፎካካሪ ሊኾኑበት ስለሚችሉ የሚጠቅመውን ተቋም ዐቅፎና አስቀጥሎ አይበጀኝም የሚለውን ያፈርሰዋል።

በኹለተኛ ደረጃ፣ ዴሞክራሲን ሊያራምዱ ይችላሉ የሚባሉትን ዐዲስ ተቋማት ይገነባል፤ ኾኖም ግን፣ ተቋማቱ በመጀመሪያ እንደ ሥርዐት የቆሙበትን መንፈስ ሽሮ ሕይወት አልባ በማድረግ ለታይታ፣ በቅርፃቸው ብቻ እውናዊ እንዲመስሉ ያደርጋቸዋል። በዚኽም ሳይገታ በራሱ ቁጥጥር ሥር ከአዋላቸው በኋላ፣ ተቋማቱን እንደ ለማዳ እንስሳ እዚያው ሥርዐቱ ግቢ ውስጥ ይለቃቅቸዋል፤ ነገር ግን እነኚኽ የተሽመደመዱና ለአገዛዙ የተገሩ ተቋማት እንዲኹ ተቀላቢ ኾነው አይቀመጡም። ሥርዐቱ እስከአለ ድረስ ትጉሃን የጭነት ፈረስ ኾነው አገልግሎታቸውን ያበረክታሉ።

በሦስተኛ ደረጃ፣ ሥርዐቱ ሲጀምር ሕገ መንግሥት ተቀርፆ በአንድ በኩል ከአሐዳዊ ወደ ፌደራላዊ ሥርዓት ሽግግር መደረጉ ተገልጧል፤ በሌላ በኩል ከአንድ ወጥ የሥልጣን ዘርፍ ወደተለያየ የሥልጣን ዘርፍ ሔዶ የሥልጣን ክፍፍል እንዲኖር በሕገ መንግሥቱ በሕግ ተደንግጓል፡፡ አሁን ምን ደረጃ ላይ ደርሰናል ብለን በምንመለከትበት ጊዜ ግን የምናገኘው የሚከተለውን እውነታ ነው። ሕግ አስፈጻሚው ክፍል ወደ ጎን (Horizontal) እና ወደ ላይ (vertical) የሥልጣን ሽሚያ በማድረግ በአንድ በኩል ፌደራል ተቋሙ ላይ በሌላ በኩል የሕግ አውጪው እና የሕግ ተርጓሚው ላይ ትልቅ ጫና በማሳረፍ ሥልጣናቸውን በእጅጉ ገድቦታል። በመኾኑም፣ በእኒኽ ኹለት ዐሥርት ዓመታት ውስጥ፣ ሕግ አስፈጻሚው ተቋም ከሌሎቹ የመንግሥት ክፍሎች ኹሉ በበለጠ እየተጠናከረ እንዲኹም ሌሎቹን ተቋማት እያመነመነ ሔዷል።

ሀ) የፍትሕ ተቋማት፡-
በማንኛውም ሀገር ታሪክና በእኛም ነባራዊ ኹኔታ እንደምንረዳው፤ ያለሕግ ነጻነት የለም። እንዲኹም ሕግን ለመተግበር የፍትሕ ተቋማት ወሳኝ ድርሻ አላቸው። ኾኖም ግን የአንድን አገር ፍትሕ ለማስከበር የሕግ ተቋማት ራሳቸው በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ የግድ ይላል። ይኸውም የራሳቸውን ልዕልና ያላስከበሩ ተቋማት የዜጎችን ነጻነት ያስከብራሉ ማለት ዘበት ስለኾነ ነው።
አንዳንድ ጸሐፍት እንደሚነግሩን፣ የጠቅላይነት ሥርዓቶች የፍትሕ ተቋማትን ልዕልናና አቋም ለመቦርቦርና ለማዳከም ሕጉን ለመጨቆኛ በሚኾን መልኩ ደጋግመው በማመቻቸት (Judicialization of repression) ሲተገብሩ ይስተዋላሉ። ይህን ለመተግበር ከሚከተሏቸው መንገዶች የተወሰኑትን እንደሚከተለው ማየት ይቻላል።

I. የፍትሕ ተቋማትን ሥልጣን መገደብ (disempowerment)፤
የፍትሕ ተቋማትን መገደብ በምንልበት ጊዜ፤ የተለያየ እመቃ ደረጃ ያለው ነው። በመጀመሪያ፣ የተሠየሙትን ዳኞች ሥልጣን መገደብና ማሳነስ ነው፤ በተጨማሪም ለመመርመር የሚችሉበትን ወሰን በእጅጉ ማጣበብና በመጨረሻም ዳኞች ሊኖራቸው የሚገባውን የውሳኔ ነጻነት (ዲስግሬሽን) ማሳጠር ማለት ነው።

II. ለመንግሥት “ይበጃሉ” የሚባሉ ሰዎችን መሠየም፤
በዚህ ረድፍ የሚታየው ኢ-ፍትሐዊ ጉዞ የሚጀመረው በዳኝነት ወንበር ላይ የሚሠየሙት ዳኞች እየተመረጡ የሥርዐቱ ወዳጆች እንዲኾኑ መደረጉ ነው። የሕዝብ አስተዳደር ጥናት ያጠኑ አንዳንድ ምሁራን እንደሚነግሩን፤ አንደኛው የመንግሥት ችሎታ፣ ለጥቅማጥቅም ቀልባቸውን ሊሰጡ የሚችሉትን ነቅሶ የማውጣት ስልት ነው። እነኚኽም ለጥቅማጥቅምና ድጎማ የተመቻቹ ሹመኞች (incentive compatibility) ናቸው። በጥቅም የማይደለሉትን ደግሞ ቀጥተኛውን መንገድ ተከትለው እንዳይሔዱ በማስፈራራት ሐሳብን የማስፈጸም ጫና (dissuasive punishment) እንዲደርስባቸው ይደረጋል። ከዚኽም በተጨማሪ የፍትሕ ሒደቱን ረጅምና ውሳኔውን ለመሻር በሚያመች መልኩ ከታች ወደ ላይ እንዲሔድ፤ እልባቱ በረጅም የአቤቱታና የውሳኔ መሻርያ ሰንሰለት እንዲፈጸም ይደረጋል።

III. የተበታተነ የፍትሕ ሥርዐት፤
ሕጉን ለመጨቆኛ በሚኾን መልኩ ማመቻቸት (Judicialization of repression) በአንድ ሀገር ያለ የፍትሕ ሥርዓት አንድ ወጥ የኾነ ቅርጽ እንዳይኖረው፣ መደበኛ ከኾነው የሕግ ተቋም ተፎካካሪና በሕግ አስፈጻሚው ቁጥጥር ሥር የኾነ መንታ ተቋም በመፍጠር የመደበኛውን ፍርድ ቤት ተግባር ወደ ተቀጽላው ተቋም ማሸጋገር ነው።

ለ) የሚዲያ ቁጥጥር፤
ሚዲያን በሚመለከት ተቀዳሚው የኦተሪተርያን መንግሥታት ዓላማ፤ ፖለቲካዊ መረጃዎችን የማምረቻ ኃይልን መቆጣጠርና በአገሩ ውስጥ ብቸኛ አምራች ኾኖ መቅረብ ነው። ዜጎች በተለይ የፖለቲካ መረጃን በአማራጭ እንዳያገኙና ተፎካካሪ የኾነ የፖለቲካ ምልከታ እንዳይኖር ፍጹማዊ ሥልጣንን የተጎናጸፉ መንግሥታት ከሚያደርጓቸው ዕቀባዎች መካከል የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል።

የመገናኛ ምንጮች ብዝኃነት በመከልከሉ ዜጎች የመገናኛ አውታር ባለቤት የመኾን ዕድል የላቸውም። በመኾኑም በአገሪቱ የሚገኙት ሚዲያዎች በመንግሥት ሥር በመኾናቸው፤ የዝግጅቱን ይዘት ለመወሰን፣ ሕዝቡ ምን መስማት እንዳለበትና ምን መስማት እንደሌለበት በቁጥጥራቸው ሥር ማድረግ ይችላሉ። አንዳንድ የሚዲያ ተቋማት ለግለሰቦች በባለቤትነት የተሰጡ ቢኾንም የትኩረት አቅጣጫቸው ጠንከር ያሉ ፖለቲካዊ ጉዳዮችን በማንሣት ወይም ወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮችን በትኩረት በመዘገብ እንዲሠሩ ስለማይፈቅድ ብዙ ጊዜ በመዝናኛ፣ በስፖርታዊ ዘገባዎችና ይህን በመሳሰሉ ጉዳዮች ላይ የታጠሩ ፕሮግራሞችን በማስተላለፍ እንዲጠመዱ ያደርጓቸዋል። ይህ ዐይነቱ የመገናኛና ሚዲያ የትኩረት አቅጣጫ ለሥርዐቱ ብዙም አስጊ ባለመኾኑ ከጫና ለመገላገል የሚጠቅም መላ ኾኖ ሲያገለግል ይስተዋላል።

ሐ. የምርጫ ሥርዓት፡-
ወደ ዴሞክራሲ ጎዳና ገብተዋል የሚባሉት አገሮች ተቀዳሚ ሥራ የሠሩት በምርጫ ተቋማት ላይ ነው። መንግሥታት በአገራቸው ሕዝብ ፊትም ኾነ በዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ፊት በፍትሐዊ ምርጫ ሥርዐትና ሒደት ውስጥ ማለፋቸው የቅቡልነት መሠረታዊ ጥያቄ ኾኗል። የምርጫ አስፈላጊነት በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌ ላይ እንኳን የሕግ ዕውቅና አግኝቶ ወቅታዊ እና እውነተኛ ምርጫ ማካሔድ የአገሮች ተቀዳሚ ሓላፊነት እንደኾነ ተቀምጧል።

በኢትዮጵያም በሕገ መንግሥቱ፣ እንደ አንድ የዴሞክራሲ ሽግግር ሒደት ውስጥ እንዳለ አገር፣ በየአምስት ዓመቱ አገሪቱን ለማስተዳደር ተፎካካሪ ፓርቲዎች በብሔራዊ ምርጫ ለመንግሥት ሥልጣን የሚወዳደሩበት ሥርዐት ተደንግጓል። ከዚኽም በመነሣት፤ የመጪው ግንቦት ወር 2007 ዓ.ም. ውድድር ብሔራዊ ምርጫ ነጻ፣ ፍትሐዊና የሕዝብ ተአማኒነት ባለው መልኩ እንዲካሔድ አቅጣጫ ተቀምጧል። የሕዝብ ተአማኒነት የሚለው እንደ መሥፈርት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተቀመጠ ስላልሆነ ለጊዜው እንተወውና፣ “ነጻ” እና “ፍትሐዊ” በሚሉት ስያሜዎች ላይ እናተኩር። ከኹሉ አስቀድሞ፣ ቃላት በመስጠትና ቃላቱን በመደጋገም ብቻ እውንና ተጨባጭ ማድረግ ይቻላል ወይ? በአኹኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ ልትጎናጸፍ ትችላለች ወይ? ስለ ነጻና ፍትሕዊ ምርጫ በመጠኑ ከአብራራኹ በኋላ፣ የጥያቄዎቹን ምላሽ ለአንባቢ እተዋለኹ።

“ነጻ” እና “ፍትሐዊ” የሚለው ቃል በመጀመሪያ ብቅ ያለው እ.ኤ.አ. በ1927 ዓ.ም. የአሜሪካን ካልቨን ኮሌጅ ልኡክ ኒኳራጓ ለምትባለው አገር “አሜሪካ ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ እንድታካሂድ ቃል እሰጣለኹ፤” የሚል ንግግር ሲያደርግ ቃሉ የመጀመሪያ ዕውቅናውን አግኝቷል። ቀጥሎም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የ1956 ዓ.ም የቶጎ ላንድን የወደፊት ኹኔታ በሕዝበ ውሳኔ ለማረጋገጥ ባወጣው ሪፖርት ላይ ይኸው ቃል ተደግሟል። በሦስተኛ ደረጃ፤ በ1978 ዓ.ም. በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ውሳኔና ቁጥጥር የናሚቢያ ነጻነት፣ ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ ከተካሔደ በኋላ ምክር ቤቱ የሒደቱን ፍትሐዊነትና ነጻ አካሔድ ለዓለም ሲያበሥር ቃላቱ ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነት ለማግኘት በቅተዋል።
ኹለቱ ስያሜዎች አብዛኛውን ጊዜ በአንድነት ቢጠቀሱም፤ ይዘታቸውንና ትርጉማቸውን በተናጠል ለማየት እሞክራለኹ፡፡

(ሀ) የምርጫ ነጻ ሒደት ሲባል፡-
ከኹሉ አስቀድሞ ነጻ የሚለው ቃል ዜጎች የማይሸራረፍ የመምረጥ መብት እንዳላቸው የሚጠቁም ነው። የዜጎችን በነጻ የመምረጥ መብት ለመተግበር የሚከተሉት ኹኔታዎች መመቻቸት አለባቸው።
1. የመሰብሰብ እና የመመካከር ነጻነት፣
2. ማኅበራትን የማቋቋም መብት፣
3. የመንቀሳቀስ መብት፣
4. የመናገር መብት፣
5. የፖለቲካ ድባቡ ከዘለፋ፣ ከማስፈራራትና ከመዋከብ የጸዳ መኾን ይኖርበታል።

(ለ) ፍትሐዊ ምርጫ ስንል ደግሞ፡-
1. ተአማኒ በኾነ የምርጫ ቦርድ ሥር የድምፅ ቆጠራው መካሔዱ፣
2. ከምርጫው በፊትም ኾነ በኋላ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል አለመግባባት ሲከሠት ፍትሐዊ የግጭት መፍትሔ የሚሰጥ ተቋም መኖሩ፣
3. ኹሉም የፖለቲካ ፓርቲዎችና ግለሰቦች ውድድር ውስጥ እንዲገቡ ያልተጨናነቀና እኩል ዕድል መስጠት፣
4. ኹሉንም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚያስተናግድ እኩል የሚዲያ አቅርቦት ማመቻቸት፣
5. የውድድሩ ሜዳ ለኹሉም ፓርቲዎች የተስተካከለ እንዲኾን ማድረግ ሲቻል፣
6. በዋናነት የመንግሥትና የፓርቲ የምርጫ ወጪ የሚወጣበት ቋት ሲለይ ነው።
ከላይ የጠቀስናቸው አንዳንድ ነጥቦች እንደሚያሳዩት፣ ነጻና ፍትሓዊ ምርጫ የሚሟላው በአንድ ቀን የድምፅ መስጫ ኮሮጆ ውስጥ ካርድ በማስገባት ሳይኾን ሦስት የምርጫ ሒደትን ሲያካትት ነው። (ሀ)ከምርጫ በፊት ያለው የአገሪቱ የፖለቲካ ድባብና የመወዳደሪያው ሜዳ መስተካከል፤ (ለ)የምርጫው ቀን ውሎ እና ገለልተኛ አወዳዳሪ ተቋም፤ (ሐ)ከምርጫው ዕለት በኋላ በተወዳዳሪዎች መካከል ጭቅጭቅ ቢነሣ ዳኝነትን የሚሰጥ ገለልተኛ ተቋም። ከላይ ላነሣነውም ጥያቄ ተገቢ ምላሽ ለማግኘት፣ አንባቢ፣ የጠቀስናቸውን መስፈርቶች ከአገራችን ነባራዊው ኹኔታ ጋራ በማነጻጸር የራሱን ፍርድ መስጠት ይችላል።
(ይቀጥላል)

The post ኢሕአዴግኣዊ ዴሞክራሲ እና ሊብራሊዝም – ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ appeared first on Zehabesha Amharic.

ማስታወቂያ ለህጻን ኢንቨስተሮች ከዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም –ክንፉ አሰፋ

$
0
0

Tewodros adhanom
አሁን የምጽፈውን በደንብ አንብቡ። መቶ በመቶ እውነተኛ ነው። እውነተኛ ኩሸት።

“ያልተገባ ነገር እየፃፍን ልጆችን አንጉዳ። ሕጻናት የምታስቡት ፕሮጀክት የተቀደሰ ነው። እንደሚሳካም እምነቴ የፀና ነው። አሁን ዋናው ጉዳይ ህጻናት ህልማቸውን እንድናሳካ የማበረታታትና የመደገፍ ነው። ሕጻናት ሆይ 20 ሚሊዮን ዶላር ባትይዙም ቢሮዬ ብቅ በሉ!”

አይቴ ቴድሮስ በፌስ ቡክ ገጻቸው የለቀቁት መልእክት ይህ አልነበረም። ይህ አሸባሪዎች በርዘው የለቀቁት እንጂ፣ የዶ/ር ቴድሮስ ትክክለኛው መልእክት እንዲህ ይነበባል።

“ያልተገባ ነገር እየፃፍን ልጅቷን ባንጐዳ፡፡ ያሰበችው ፕሮጀክት የተቀደሰ ነው እንደሚሳካም እምነቴ የፀና ነው፡፡ አሁን ዋናው ጉዳይ በሪቱ ጃለታ አሕመድ ህልሟን እንድታሳካ የማበረታታትና የመደገፍ ነው፡፡ Galatoomaa በሪቱ፡፡ አላህ ይባርክሽ፡፡ Rabbi si haaeebbisu በርቺ፡፡ Jabaadhuu”

በማህበራዊ ድር-ገጾች ብዙ ፉገራዎች ከተራው ሰው ሲሰራጩ ቢታዩም፤ ነጭ ፉገራን በሚንስትር ደረጃ ስናይ ግን የመጀመርያው መሆኑ ነው።

በፌስቡክ ላይ “የጀርመን ነዋሪ ነኝ” ያለችው ልጅ ፒያሳ ባር ስታስተናግድ ተገኘች። የፌስቡክ ጓደኞችዋ በድንገት ሲያገኟት ልጅት ምንም አልመሰላት። “ለምን ዋሸሽ?” ቢሉዋት። አይኗን በጨው አጥባ መልስ ሰጠች።

“መዋሸት ብርቅ ነው እንዴ?” አለች። የሷን ፉገራ በመቶ እጅ የሚበልጡ ፉገራዎች ስለሚያጽናኗት ቅንጣት ያህል አልደነገጠችም። ጣትዋን በቴድሮስ አድሃኖም ላይ እያነጣጠረች ጓደኞችዋን አረጋጋች።

የዚህችን ወጣት ውሸት ማካበድ እንደማያስፈልግ የተረዱት ጓደኞችዋ፣ ከውቅያኖስ የጠለቀውን፣ ከባህር የሰፋውን የቴድሮስ ውሸት ከሰሙ በኋላ ነበር።

“አበስኩ ገበርኩ… የባሰ አታምጣ።” ይላሉ እናቶች።

በአጼ ምኒሊክ ግዜ ለፍርድ ሙግት የቀረበ አንድ ሰው እጁን እያወራጨ ሲናገር ብብቱ ይታይ ነበር። እብብቱ ስር ያለ ጸጉሩም አጎፍሮ ነበር። የብብቱን ጸጉር ያስተዋሉ ዳኛ፣ ችሎት በመድፈር ወንጀል 50 ጅራፍ ቀጡት። ሰውየው ቅጣቱን ሳይግደረደር ተቀበለ። ይህንን 50 ጅራፍ ለምን ሳይከላከል እንደጠቀበለ በጓደኛው ሲጠየቅ፣ ለብብቴ 50 የቀጡኝ የታችኛውን (የሃፍረተ ስጋዬን) ጎፈር ቢያዩ 100 ይሉኝ ነበር አለ።

“… የባሰ አታምጣ።” ነው ነገሩ።

ከዚህች ተራ ወጣት የባሰው ነጭ ውሸት በተጋለጠ ጊዜ፣
“የ14 አመትዋ ልጅ በአውስትራሊያ የ8ኛ ክፍል አስደናቂ ውጤት በማምስመዝገብ ያገኘችውን 20 ሚሊዮን ዶላር በኢትዮጵያ ለልማት ለማዋል ወሰናለች ያልኩት ፍጹም ስህተት ነው። ስለ ጥፋቴ የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ እጠይቃለሁ።” ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ተናገሩ።

የሚል ዜና ብንጠብቅ፣ ብንጠብቅ፣ ብንጠብቅ እስካሁን ልንሰማ አልቻልንም። አቤ ጎርጉሮ ያወጣውን ቅሌት በፌስቡክ ከተለቀቀው የልደት ውስኪያቸው ጋር አወራርደውታል። ውሸቱ አሸማቆ፣ አሸማቆ፣ ይገድላቸዋል… ድንጋጤው ይጥላቸዋል ብሎ የገመተ ጥቂት አይደለም። ግን እንዴት አይነት ፈጣጣ ናቸው። ያንን ጉድ ይዘው ቢሮ ሲገቡ ምንም እንዳልተፈጠረ መስለው ብቻ አይደለም። ውሸታቸውን ስልቅጥ፣ዋጥ አድርገዋት ሌላ ጥፋት ደረቡበት።
“ህጻናትን ወደኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው።” የሚለውን የክርስቶስ ጥቅስ ቀየር አድርገው የራሳቸውን ፈንጠዝያ ሊነግሩን ሞከሩ።

“…ህፃናትና ታደጊዎች የዋሆች እንደሆኑ ክፋት እንደሌላቸው ከኔ ጋር የምትስማሙ ይመስለኛል። በዚህ ምክንያትም ህፃናትና ታዳጊዎች የሚነግሩኝን ማመን እመርጣለሁ። ስህተትም ቢኖራቸው ከየዋህነት ካልሆነ ከክፋት አይመነጭም። ህፃናትን ማመን ስህተት ከሆነ መሳሳትን እመርጣለሁ።…”

አይቴ ቴድሮስ በዚያ በልካቸው ባልተሰራ ወንበር ላይ ተቀምጠው ከሰሞኑ በርካታ ህጻናትን እንደሚያስተናግዱ ይጠበቃል። ከውጭም ከሃገር ውስጥም ኢቨስተር ህጻናት ወደ ቴድሮስ ቢሮ ይጎርፋሉ። በሚሊዮን እና በቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት እናደርጋለን ብለው ይዋሻሉ። ቴድሮስም በፌስ ቡክ ገጻቸው ታሪኩን ይለቀልቁልናል…ውሸቱንም ይለቁልናል። እነሆ ህጻናትን ማመን ስህተት አይደለምና እንዲዋሹ ተፈቅዶላቸዋል።

አፍ ሲከፈት ጭንቅላት ይታያል የሚባለው እውነት ነው። ጭንቅላት ሲገለጥ ደግሞ ገመና ይወጣል። በህወሃት መዋሸት አዲስ ነገር አይደለም። ሰዎቹ በቀን ከመቶ ግዜ በላይ ይዋሻሉ። በስነልቦና ተመራማሪዎች እነዚህን ሰዎች ፓቶሎጂካል ውሸታሞሽ ይላቸዋል። ይህ በሽታ ሰዎች ካሉበት ችግር ለማምለጥ ወይንም ከተቆራኛቸው የበታችነት ስሜት ይመጣል። ውሸት መናገር፥ አንዳች ጥቅም ለማግኘት ሲባል ሆን ተብሎ የሚፈፀም ድርጊት ነው። ለዚህ የስነ ልቦና ችግር ከጥቅሙ ይልቅ የረጅም ጊዜ ጉዳቱ ያመዝናል። የሚዋሸው ሰው በሰዎች ዘንድ የሚኖረውን ተቀባይነትን የሚያሳጣ ስብዕናም ያላብሳል። ችግሩ የስነልቦና ነውና መፍትሄውም የስነ-ልቦና ህክምና ነው።

አንድ አባት ልጁን ይጠራውና “ልጄ፣ ጥፋት ካጠፋህ የቤታችን ውሻ ስለሚነግረኝ ተጠንቀቅ።”ይለዋል። ልጁ ውሻ የሚሰማ እና የሚናገር ይመስለው ኖሮ ውሻውን እየቀረበ ያናግረው ነበር። ነብስ እስኪዘራ ድረስም ይህንን ውሽት አምኖ ተሸወደ።

የቴዎድሮስ አድሃኖም ግን ተገላቢጦሽ ሆነብን። ነብስ እስኪዘራ ድረስ… ህዝቡን መሸወድ ተያይዞታል። በዚህ የመረጃ ዘመን ነጭ ውሸት ዋሽቶ ሲያበቃ፣ ውሸቱ ሲነቃ ሌላ ታሪክ መፍጠር ህዝቡን ዝቅ አድርጎ መመልከት አይመስልም? 20 ሚሊየን ዶላር እኮ ከ20ሺ ዶላር ይበልጣል። 20 ሚሊዮን ዶላር ከ 200 ሺም ይበልጣል። 20 ሚሊዮን ከ 2 ሚሊዮንም በ10 እጥፍ ይበልጣል። 20 ሚሊዮን በጣም ተጋነነ። ከአንድ ጀምረው ቀስ በቀስ እያሳደጉ ወደዚያ ቢደርሱም አንድ ነገር ነው።

ጃፓኖች እንዲህ ይላሉ። “የሚታመን ውሸት ለመዋሸት ከፈለግህ የማይታመን እውነት አትናገር።”
አይቴ ቴድሮስ በቅድሚያ ውሸትን በማንኪያ… ውሸትን በትንሹ ያለማምዱን! … ታዲያ እንደጀመሩ ይጨርሱልን።

The post ማስታወቂያ ለህጻን ኢንቨስተሮች ከዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም – ክንፉ አሰፋ appeared first on Zehabesha Amharic.

ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ለአቶ ኤርሚያስ ለገሰ የሰጠው ምላሽ: ኤርምያስ ኤርምያስ ሆይ!

$
0
0

የኤርምያስ ለገሠን ‹ግልጽ ደብዳቤ› አነበብኩት፡፡ አንብቤው በሁለት ምክንያት ሳልጽፍለት ዘገየሁ፡፡ በአንድ በኩል ስለ ኤርምያስ ከነበረኝ የዋሕ ግምት የተነሣ ኤርምያስን ያህል ሰው ይህን ያህል አይሳሳትምና በቀጣዮቹ ቀናት በስሜ የወጣ ጽሑፍ ነው እንጂ የጻፍኩት እኔ አይደለሁም ይል ይሆናል ብዬ በመገመት፡፡ ጽሑፉ እንደወጣ ብዙ ሰዎች አሁን እኔ የምነግርህን ሲገልጡት ነበርና ትሰማቸዋለህ ብዬ አስቤ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የሐዲስ ዓለማየሁ የባሕል ማዕከል ባዘጋጀው ዐውደ ጥናት ላይ ልካፈል ወደ ደብረ ማርቆስ ተጉዤ ስነበር፡፡ 
daniel-kibret-300x207
ከደብረ ማርቆስ ተመልሼ ገጸ ድሮቹን ሳሥሥ ግን ኤርምያስ ከነ ስህተቱ ጸንቶ አገኘሁት፡፡ ገሥግሦ የመጣን ደኅና አድርገህ ጫነው ነውና ለዚህ ሰው መንገር ያለብኝ ነገር አለ ብዬ አሰብኩ፡፡

ይህን ‹ግልጽ ደብዳቤ› ኤርምያስ አይጽፈውም ያልኩት እንዲህ ጊዜና ሁኔታን የማያገናዝብ ሰው ነው ብዬ ስላልገመትኩት ነው፡፡ አንድን ጽሑፍ ለመጻፍ ሲል ብቻ የሚጽፍ ሰው አድርጌ ስላልገመትኩትም ነው፡፡ ያንን መጽሐፉን በዕውቀትና በመረጃ ስለመሰለኝ ‹ቅዳሴው አልቆብህ ቀረርቶ ትሞላበታለህ› ብዬ ስላላመንኩ ነው፡፡

ኤርምያስ ሆይ፤

ይሄ አሁን አንተ አይተህ የደነገጥክለት ጽሑፍ አንተ ባዳመጥከው ጊዜ (በ2007 ዓም) የቀረበ ጥናት አይደለም፡፡ ምናልባት ‹ምንትስ የሰማ ለት ያብዳል› ሆኖብህ ካልሆነ በቀር፡፡ ጽሑፉ የቀረበው ነሐሴ 25 ቀን 1999 ዓም አሜሪካ፣ ዴንቨር ኮሎራዶ ከተማ ተደርጎ በነበረው ሰባተኛው የአሜሪካ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ ነው፡፡ የተለቀቀው ደግሞ ከአንድ ወይም ከሁለት ቀን በኋላ www.tewahedo.org በተሰኘ ገጸ ድር ነው፡፡

በዚያ ጥናት ውስጥ ‹አክራሪነት› የተፈረጀው ከእምነት አንጻር ነው፡፡ አክራሪ እስላም ስልም ‹‹በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ ሆን ብሎ የጥፋት ዓላማ በመያዝ፣ የሕዝቡን አብሮ ተገናዝቦ የመኖር ሥርዓት በማፍረስ፣ አንዳንዴም የሌሎችን ዓላማ በማንገብና የቤት ሥራ በመውሰድ የተሠማራውንና እስልምናን ሽፋን የሚያደርገውን የጥፋት ኃይል ነው›››፡፡ ክርስቲያኖች ሁሉ ቅዱሳን ናቸው እንደማልለው ሁሉ ሙስሊሞች ሁሉ አክራሪዎች ናቸው ብዬ አላውቅም፡፡ አልልምም፡፡ ምክያቱም፣ ስላልሆነ፡፡

እስከ 2002 ዓ.ም ያለው ወቅት ማለት ደግሞ አንተ ራስህ በመጽሐፍህ እንደነካካኸው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ለማየት በማይፈልጉ ‹አክራሪ ሙስሊሞች› ቦታዋን የመንጠቅ፣ ካህናቷን የማረድ፣ ገዳማቷን የማቃጠል፣ ቅዱሳት መጻሕፍቷን የመዝረፍና ወደ ባዕድ ሀገር የማሻገር እኩይ ተግባር ይከናወን የነበረበት፣ እንዲያውም ሁኔታው ራሱ ጫፍ የደረሰበት ጊዜ ነበር፡፡

አንተ ዛሬ ስትወጣ በሌሎች ብቻ አመካኘኸው እንጂ በአዲስ አበባ አየር ጤና ኪዳነ ምሕረት የጥምቀት ቦታ ክርክር ጊዜ የመንግሥትን ሥልጣን ይጠቀሙ ከነበሩት ሰዎች አንዱ ነበርክ፡፡ በወቅቱ እኔ የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያዎች ኃላፊ ነበርኩ፡፡ ጉዳዩን ከእግር እስከ ራሱ ዐውቀው፣ እከታተለውም ነበር፡፡ መረጃዎቹንም ከየአቅጣጫው እናገኝ ነበር፡፡ አጠናቅረንም በጋዜጣ እናወጣ ነበር፡፡ በዚያም ምክንያት አያሌ ጫናዎችን ካደረሱብን ሰዎች አንዱ አንተ ነበርክ፡፡ ቢሮህ አስጠርተህን ቤተ ክርስቲያኒቱንና የፈረደበትን አማራ ምን ብለህ እንደተሳደብክ  የምናውቀው አንተ እና እኛ ነን፡፡

ከአሰቦት መነኮሳት የ1984 ዓም መታረድ በኋላ በሚዲያ ዋና ክፍል እኔና ጓደኞቼ ከሠራናቸው ሥራዎች መካከል አንዱ አክራሪ ሙስሊሞች በቤተ ክርስቲያኒቱ ከጥንት እስከ ዛሬ ያደረሱትን፣ ሊያደርሱትም ያሰቡትን መረጃ ማሰባሰብ ነው፡፡ አንዳንዶቹን በቦታው ተገኝተን፣ ሌሎቹን ከቦታው በሚመጡ መረጃዎች፣ የቀሩትንም ከተለያዩ የመረጃ ምጮች አሰባስበናቸው ነበር፡፡ ከሚመለከታቸው የውጭ ዩኒቨርሲቲዎችና የመረጃ ምንጮችም በውድ ዋጋ የገዛናቸው ነበሩ፡፡

በነገራችን ላይ ያ ጽሑፍ በፕሮጀክተር ታግዞ ቀርቦ ስለነበር የመረጃ ምንጮቹን የሚያሳየው የጎንዮሽ ማስተዋሻን ማንበብ አላስፈለገም፡፡ ለዚህ ነው ምንጩን የድምጹ መልእክት ላይ ያላገኘኸው፡፡ የድምጹን መልእክት የለቀቅኩትም እኔ አልነበርኩም፡፡ የኦርቶዶክስን ትምህርቶች በመረጃ መረብ በመልቀቅ የሚታወቀው www.tewahedo.org የተሰኘ ገጸ ድር ነው፡፡ ዛሬም በዚሁ ገጸ ድር ላይ ስላለ ማየት ትችላለህ፡፡ ወይም አዘጋጁን በገጸ ድሩ ላይ ባሠፈረው የመመየሊያ አድራሻው(email)ብትጠይቀው የሚነግርህ ይመስለኛል፡፡

አንተን ወደ ባሰው ስሕተት የወሰደህ የተሟላ መረጃ ሳታገኝና ለማግኘትም ሳትፈልግ ወደ ድምዳሜ መንደርደርህ ነው፡፡ የመጀመሪያው፣ እኔ ጥናቱን በ1999 ዓም ዴንቨር ኮሎራዶ፣ በ2000 ዓም አዲስ አበባ ደብረ ገሊላ ዐማኑኤል ቤተ ክርስቲያንና በዮርዳኖስ ሆቴል (ማኅበሩ ስለ ሚሊኒየም ባዘጋጀው ጉባኤ) ካቀረብኩት በኋላ ነው ‹ሽመልስ ከማል ሠራው› ያልከው ጥናት ለመንግሥት የቀረበው፡፡ ያ ጥናት ለመንግሥት አካላት ሳይለዋወጥ መቅረቡን በወፍ በረር እናውቅ ነበር፡፡ ስለዚህም የተከተለ ከቀደመ ይወስዳል እንጂ የቀደመ ከተከተለ አይወስድምና ‹ቃላት ሳይቀየሩ የቀረበው› እኔ ያቀረብኩት ጽሑፍ እንጂ በእናንተ ስብሰባ ላይ የቀረበው ጽሑፍ ወደ እኔ መጥቶ ሊሆን አይችልም፡፡ አንተ ራስህ በመጽሐፍህ ውስጥ አድንቀህ የጠቀስከው የአቡነ ሳሙኤል መጽሐፍኮ ይህንን ዋቤ አድርጎ የተጻፈ ነበር፡፡ እርሳቸውም ‹ከሽመልስ ከማል ወስደው› ነው ልትል ነው?

ሁለተኛው ስሕተትህ ቤተ ክርስቲያኒቱንና የቤተ ክርስቲያኒቱን ልጆች የምታይበት ዓይንህ ዛሬም አለመስተካከሉን የሚያሳየው ስሕተት ነው፡፡ ይህቺ ቤተ ክርስቲያን የሚቆረቆሩ ብቻ ሳይሆኑ መሥዋዕት ሆነውም ታሪክ የሚሠሩ ልጆች አሏት፡፡ እነዚያ ልጆች ናቸው አይገቡ ገብተው እነዚያን መረጃዎች የሰበሰቧቸው፡፡ አንዳንዶቹን መረጃዎች ለማግኘት እንደ ሠለስቱ ደቂቅ በእሳት ውስጥ ማለፍን ይጠይቅ ነበር፡፡ አንተና ሌሎቻችሁም የደነገጣችሁት ‹‹ሰው በቅንዐተ እምነት ተነሣስቶ እንዲህ አይሠራም፣ ሌላ ከጀርባው አንድ ነገር አለ›› ብላችሁ ስለምታምኑ ነው፡፡

በበሻሻ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ጅማ ውስጥ በጥቅምት 1998 ዓም አክራሪ ሙስሊሞች በየዋሐን ምእመናንና ካህናት ላይ የፈጸሙትን ግድያ ሕዝቡ ሲሰማኮ አንተና ሌሎቻችሁም ጣታችሁን እኛ ላይ ጠቁማችሁ ስንት ቀን እሥር ቤት አመላልሳችሁናል፡፡ አንተ ራስህ በመጽሐፍህ የገለጥከው ራስህ ቆመህ ያስፈረስከውን ቤተ ክርስቲያን በተመለከተ በድፍረት መጀመሪያ የዘገብነው በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ ላይ ነበር፡፡ ያኔ ምን እንዳላችሁን ታውቃለህ፡፡

ሦስተኛው ስሕተትህ ‹የዶክተር ሺፈራው ጥናት ለምን በአንተ ጥናት ውስጥ አልቀረበም?› የሚለው ነው፡፡ ለምን ይቀርባል? እኔኮ የራሴን ጥናት ሠርቼ በራሴ መድረክ ላይ ነው ያቀረብኩት፡፡ 1999 ዓም ከ2001 ዓም በኋላ የሚመጣ ነው ካላልከኝ በስተቀር፤ በኋላ የተደረገ ጥናት እንዴት ተደርጎ ነው በፊት በተሠራ ጥናት ውስጥ የሚካተተው?

የዛሬ 8 ዓመት ጥናቱ ሲሠራ ያገኘናቸውንና ያመንባቸውን መረጃዎች ተጠቅመናል፡፡ ያ ማለት ግን ሁሉን ዐውቀን ነበር ማለት አይደለም፡፡ አንተ ጉዳዩን ሲያባብሱ ነበሩ ያልካቸው ባለ ሥልጣናት አክራሪነትን ሲመሩትና ሲያቀጣጥሉት ነበር ካልክ መረጃውን በበቂ ሁኔታ አንተ በቦታው የነበርከው ንገረን፡፡ ከዚያ ውጭ መከላከያ ሠራዊት ያደረገውን ጥረት ግን በአካል በመገኘት ጭምር ዐውቀዋለሁና ልዋሽ አልችልም፡፡ የተወሰኑ የመንግሥት አካላት የወሰዱትን በጎ ርምጃም ልዋሸው አልችልም፡፡ እውነት ነበርና፡፡

እጅግ ያስገረመኝ ደግሞ ‹በጥናታዊ ጽሑፍህ አሁን ያለውን የሙስሊሞች ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለምን አላነሣህም?› ብለህ የጠየቅከው ጥያቄ ነው፡፡ ለመሆኑ ይኼ እንቅስቃሴ ጥናቱ በቀረበበት በ1999 ዓም  ተነሥቶ ነበር? ወይስ ለምን ወደፊት ይመጣል ብለህ ትንቢት ለምን አልተናገርክም ማለትህ ነው? ስሜ ነው እንጂ እኔኮ ነቢይ አይደለሁም፡፡ እንዲያ ከሆነ ደግሞ አንተም ስምህ የነቢይ ነውና በኋላ በኢሕአዴግ ውስጥ ደረሰ የምትለውን ችግር ቀድመህ ዐውቀህ ለምን ከአባልነት አልታቀብክም? የሚል ጥያቄውን ስትመልስ እመልስልሃለሁ፡፡

ስለ ‹ስደተኛው ሲኖዶስ› አቋሜን በተደጋጋሚ ገልጫለሁ፡፡ የፖለቲካውን ገጽታ አንተ ንገረን፡፡ በክርስትናው ግን መንጋውን ጥሎ የሚሄድን እረኛ ጻድቅ የሚያሰኝ ነገር ስላላገኘሁ ነው፡፡ ‹የቅዱስ ሲኖዶስ መንበሩ አዲስ አበባ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ነው› የሚለው የቅዱስ ሲኖዶስ ደንብ የወጣውኮ አሁን በስደት ያሉት አንጋፋዎቹ አባቶች አዲስ አበባ እያሉ በ1972 ዓም ነው፡፡ ያንን የማክበር ግዴታ የሁሉም ነው፡፡ ‹አባት አንጂ መንበር አይሰደድም› የሚለው ደግሞ ዛሬም ነገም አቋሜ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች እንኳን ተሰድደው ፓርቲ አቋቋሙ እንጂ መንግሥት አላቋቋሙም፡፡ በምን ቀኖናዊ መብት ነው ተሰድዶ መንበር ማቋቋም የሚቻለው? ከመንበሩ ውጭ ሆኖ ሀገረ ስብከቱን ያስተዳደረ አንድ ሲኖዶስ እስኪ በታሪክ ይጠቀስልኝ? እኔ አንተን ጥቀስ ብዬ አላስቸግርህም፡፡

‹መንግሥት በቅዱስ ሲኖዶስ ጫና ማድረጉና ጣልቃ መግባቱ› ተቀባይነት የሌለውና የምእመናንን ገድል የሚጠይቅ መሆኑ ባይካድም አሁን ያሉትን አበው ብቻ የሚመለከት ወቀሳ ግን አይደለም፡፡ ለቤተ ክርስቲያናችን አንዱ የዘመኑ ተግዳሮት ብሔራዊ ሲኖዶስ ከተቋቋመ ጀምሮ ከመንግሥት ተጽዕኖ ነጻ የሆነ ሲኖዶስ አለመኖሩ ነው፡፡ ያ ማለት ግን ለእምነታቸው የሚሞቱ፣ ለእውነት የሚሟገቱ አበው በቅዱስ ሲኖዶስ ውስጥ የሉም ማለት አይደለም፡፡ አንተ ራስህ ይህንን በመጽሐፍህ ስለጠቀስከው ለቀባሪ አላረዳም፡፡

እዚህ ላይ ግን በግልጽ ልነግርህ የምችለው የመንግሥት ባለ ሥልጣናት በተወሰኑ አባቶች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርሱ ይችሉ ይሆናል እንጂ አንተ እንዳልከው ቅዱስ ሲኖዶሱን እስከ ማሽርከር የሚደርስ ዐቅም ፈጽሞ የላቸውም፡፡ቢኖራቸው ኖሮ አንተ ራስህ ተገኝተህ የታዘብከውን የአባቶች ጥንካሬ ማየት አትችልም ነበር፡፡ በ2006 ዓም በሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ የተገኙትን የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ተወካዮች በመረጃና ማስረጃ ሲወጥሩ፣ እምነታቸውን ሲመሰክሩና ያለ ፍርሃት ሲናገሩ እኔ ራሴ አባቶቼን በዓይኔ አይቻቸዋለሁ፡፡ ይህን ያደረጉት አሜሪካ ሆነው አይደለም፡፡ በቢላዋው ሥር ሆነው እንጂ፡፡

‹ለምን አሁን ቀረበ?› ብለህ የጠየቅከኝ በ2000 ዓም ቢሆን ኖሮ አብራራልህ ነበር፡፡ ጥናቱ የቀረበው በ1999 ዓም፣ አንተ ጥያቄውን ያነሣኸው ደግሞ በ2007 በመሆኑ ‹ይለፈኝ› እልሃለሁ እንደ ጋይንት ሰው፡፡

በመጨረሻ ኤርምያስ ሆይ

‹ብለነው ብለነው የተውነው ነገር

ባሏ ትናንት ሰምቶ ታንቆ ሊሞት ነበር›

የተባለው ደርሶብህ፤ ማጣሪያና ማብራሪያ ሳታገኝ ወርደህ በመጻፍህ፤ ገረመኝም አሳዘነኝም፡፡ የገረመኝ ‹አንተን የሚያህል› ብዬ የማስብህ ሰው ሁለቴ እንኳን ሳይለካ ለመቁረጥ በመቸኮሉ፤ ያሳዘነኝ ደግሞ ‹ኤርምያስ ሌላውንም ነገር የሚነግረን እንዲህ አመክንዮአዊ ሐሰት ይዞ ነው ማለት ነው› እንድል ስላደረገኝ ነው፡፡ አመክንዮአዊ ሐሰት ማለት በአቀራረቡ ተጠየቃዊ የሆነ፣ ነገር ግን በስሕተት መረጃዎች የተሞላ ማለት ነው፡፡

በመጨረሻ ዳዊት ለሳዖል የዘመረውን መዝሙር ልጋብዝህ

‹ኃያላን እንዴት ወደቁ›

 

The post ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ለአቶ ኤርሚያስ ለገሰ የሰጠው ምላሽ: ኤርምያስ ኤርምያስ ሆይ! appeared first on Zehabesha Amharic.

ልማታዊው ጓደኛዬ –ከዋስይሁን ተስፋዬ

$
0
0

የካቲት 26 ቀን፣ 2007 እ.ኢ.አ.

ጥንት አባቶቻችን እንደሚሉት “ነገርን ነገር ያነሳዋል…” ነውና፤ በአንድ ያልታሰበ አጋጣሚ እንደቀልድ ከአንድ የምወደው የቀድሞ ወዳጄ ጋር በዋዛ ፈዛዛ ያደረኳቸው ጨዋታዎች፤ እውነትም በምንወዳትና በምንሳሳላት ሃገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት እየተከናወነ የሚገኘውን ነባራዊ እውነታ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ስለመሰለኝ፤ ይህንኑ ለአንባቢያን ፍርድ ማቅረብን ወደድሁ። ነገሩ እንዲህ ነው…!

የዛሬ ሁለት ወር አካባቢነው። ከአመታት በፊት፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሳለን የቅርብ ወዳጄ የነበረ ጓደኛዬን ፌስቡክ ላይ ባጋጣሚ አገኘሁት። ለአመታት ሳንገናኝ በመቆየታችን ናፍቆታችንን ለመወጣት ይመስላል፤ በጓደኝነት ያሳለፍናቸውን ጊዜአት በትዝታ መልክ እያስታወስን ስናወጋ ለሳአታት ቆይተን ነበር። ይህ ወዳጄ ዝምተኛ የሚባሉ ከነበሩ ተማሪዎች መካከል የሚመደብ ሲሆን፤ እንደኔ በሚቀርቡት ወዳጆቹ ግን በጨዋታ መሃል ሳይታሰብ ጣል በሚያደርጋቸው አስቂኝ ቃላቶቹ ይታወቃል። እንደነገረኝ ከሆነ በአሁኑ ሰአት ከዩኒቨርሲቲ በተመረቀበት ሙያ እያገለገለ ሳይሆን፤ ያዋጣል ብሎ ባሰበው የንግድ ስራ ላይ ተሰማርቶ እየሰራ ይገኛል። በመሆኑም አንድ መለስተኛ ህንፃንና ሁለት የንግድ ድርጅቶችን በባለቤትነት ያስተዳድራል። ይህ ወዳጄ ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባትም ሆኗል። በኔ ግምት እንደተመረጡት ቁንጮ ባለስልጣናት የናጠጠ ሃብታም ባይሆንም፤ ጥሩ ኑሮን ይኖራሉ ከሚባሉት ጥቂት ዜጐች ተርታ የሚመደብ ይመስለኛል።

ባልሳሳት ለአንድ ሰአት ያክል ፌስቡክ ላይ በፅሁፍ በመመላለስ እንዳወጋን፤ ጓደኛዬ “የበለጠ እየተያየን ብናወጋ የተሻለ ይሆናል” በሚል እሳቤ፤ ወደ ስካይፕ እንድንሄድ ጠየቀኝ። እኔም ተስማምቼ ጨዋታችንን በስካይፕ ቀጠልን። በአካል ስመለከተው በፅሁፍ የነገረኝ የኑሮ ደረጃ ላይ እንዳለ ሰው የተመቸው አይመስልም። በውስጤ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ብዬ እያሰላሰልኩ ጨዋታችንን ቀጠልን።

ለአመታት የተለየሁትንና ያላየሁትን ወዳጄን እያየሁት ማውራት በመቻሌ እጅግ ተደስቼ የነበረ ቢሆንም፤ ለጥቂት ደቂቃዎች ከተጫወትን በሗላ ምናልባትም ለወዳጄ አስጊ ሊሆን የሚችል ነገር ትዝ አለኝ። ነገሩ እንዲህ ነው፤ የዛሬ ሁለት አመት አካባቢ አብሮኝ የሚሰራ አንድ ሐበሻ “ኢትዮጵያ ውስጥ በስካይፕ መነጋገር በህግ ያስቀጣል።” የሚል ህግ እንደተደነገገ የነገረኝን አስታወስኩ። መረጃውን ያካፈለኝ ባልደረባዬ እንደኔው ተሰዶ በውጭ ሃገር የሚኖር ስለነበረ ትክክለኛ ስለመሆኑ እርግጠኛ ባልሆንም፤ ጉዳዩ ለወዳጄ ደህንነት ወሳኝ እንደሆነ ስለተረዳሁ፤ ስለመረጃው እውነትነት እርግጠኛ አለመሆኔን በመናገር እንዲያረጋግጥልኝ በጥያቄ አቀረብኩለት። “እኔምልህ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በስካይፕ መነጋገር ክልክል አይደለም እንዴ !?” የመንግስታችንን አይምሬነት ስለምገነዘብ፤ እርሱም ቢያንስ ከእኔ በላይ ይጨነቅበታል ብዬ ያመንኩበት ወዳጄ፤ ፈጠን ብሎ “ባክህ እርሳው፤ መንግስታችን የሚያወጣው ህግ ከጐኑ ላጲስ አለው” ቢለኝ በጣም ተገረምኩ።

የተናገረውን በሚገባ የሰማሁት ቢሆንም፤ በመልሱ ግራ ስለተጋባሁ “ምን አልከኝ!?” አልኩት። ጓደኛዬም ነገሩ እንግዳ እንደሆነብኝ ስለተረዳ ጉሮሮውን ሳል ሳል አደረገና “ስለዚህ ጉዳይ የማያውቅ ኢትዮጵያዊ አለ ብዬ አስቤም አላውቅ። እውነትም ከሃገር ርቀሃል ጃል!” በማለት ጨዋታውን ቀጠለ። “በአሁኑ ሰአት ኢትዮጵያ ውስጥ የተደነገገ ማንኛውም ህግ ላጲስ ከጐኑ አለ እኮ ነው የምልክ! አልሰማህም እንዴ!?” ብሎ በመገረም ጥያቄዬን በጥያቄ መለሰልኝ። ወዳጄ አሁንም ያን ቀልዱን አለመተዉን ለቅፅበት አሰብ አረኩና፤ ጨዋታውን እንዲቀጥልልኝ ስለፈለኩ “ኧረ በጭራሽ አልሰማሁም፤ ደግሞ ይህ ምን ማለት ይሆን!?” ፤ “አይ አንተ ልጅ አሁንም ቀልድህን አልተውክም ማለት ነው!?” ጠየኩት። ወዳጄም ፈገግ ካለ በሗላ፤ ቀጠለ “አየህ ባሁኑ ሰአት እዚህ ሃገር ላይ ማንኛውም ወንጀል ብትሰራ በህግ አትቀጣም።”፤ “ማለቴ የመንግስታችንን አስተዳደር እስካልተጋፋህ ድረስ።”
ብዙ ጊዜ በጨዋታ መሃል ቀልድ ቢጤ ጣል ማድረግ ስለሚወድ፤ አሁንም ይህንኑ የሚያደርግ መስሎኝ የነበረ ቢሆንም፤ እርሱ ግን ፊቱን አኮሳትሮ፣ ግንባሩን አቀጭሞ ንግግሩን ቀጠለ፤ “መንግስታችን ከህገ መንግስቱ ጀምሮ በርካታ ህጐችን በወረቀት ላይ በግልፅ አስፍሯል። ነገር ግን እነዚህን ህጐች ከመንግስት ጀምሮ ማንም አያከብራቸውም፤ አይተገብራቸውምም።” የሚያጫውተኝ ቁምነገር በቀልዱ የማቀው የቅርብ ወዳጄ የነበረ ሰው ያልተጠበቀ ሲሬስነት ጋር ተጣምረው፤ ለንግግሩ ሙሉ በሙሉ አትኩሮቴን እንድሰጥ ስላስገደዱኝ፤ ሳላስበው በተመስጥኦ ማዳመጥ ጀመርኩ። እርሱ ግን መናገሩን አላቋረጠም። “መንግስትን ጨምሮ ሁላችንም ህግ እንጥሳለን፤ ምክንያቱም የምንጠየቅበት መች እንደሆነ እናውቃለና!” በአትኩሮት አይን አይኔን እያየ ንግግሩን ቀጠለ፤ “እኔ ራሴ በቀን ብዙ ህጐችን እጥሳለሁ፤ ይህን ደግሞ መንግስት በሚገባ ያውቃል፤ ግን ማንም ጠይቆኝ አያውቅም።” “አየህ እኔ ልማታዊ ዜጋ ነኝ፤ ልማታዊ ዜጋ ታውቃለህ!?” በማለት ያልጠበኩትን ጥያቄ ሲያቀርብልኝ ከእንቅልፌ የነቃሁ ያክል፤ “ኧረ በጭራሽ! ቀጥል!?” አልኩት። በርግጥ በአሁኑ ሰአት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች “ልማታዊ ጋዜጠኞች” እንደሚባሉ ስለማውቅ፤ “ልማታዊ ዜጋ” ምን እንደሆነ መገመትና መናገር እችል ነበር። ነገር ግን ጨዋታውን የሚያቋርጥብኝ ስለመሰለኝ ባጭሩ “ቀጥል” አልኩት።

ጨዋታውን ለመስማት መጓጓቴ እንዳስገረመው ከፊቱ ላይ በሚነበብ መልኩ ቀና ብሎ ካየኝ በሗላ ንግግሩን ቀጠለ፤ “አየህ እኔ ‘ልማታዊ ዜጋ’ ስለሆንኩ፤ በመንግስታችን ስራ ጣልቃ አልገባም። ያሻውን ቢያደርግ አርሱ የኔ ጉዳይ አይደለም፤ አይመለከተኝምም።” እያዳመጥኩት እንደሆነ ከረጋገጠ በሗላ በተመስጥኦ ጨዋታውን ቀጠለ፤ “ገባህ ከእኔ የሚጠበቀው፤ የተፈቀደልኝን ብቻ እየሰራሁ እስከተፈቀደልኝ ድረስ ‘በሠላም’ መኖር ብቻ ነው። እንዳልኩህ በመንግስት የስራ ጉዳይ ውስጥ በፍፁም ጣልቃ መግባት የለብኝም፤ የኔ ስራም ለዚህ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ነው፤ አለበለዚያ የምሰራቸው ወንጀሎች ያስጠይቁኛል።”

ለአፍታ አቀርቅሮ ካሰበ በሗላ፤ አትኩሮ እየተመለከተኝ ጨዋታውን ቀጠለ፤ “ሌላው የኔ ስራ ደግሞ፤ ምርጫ ሲደርስ መንግስትን መምረጥ፤ ዜጐች ቢበደሉ፤ ሃገር ቢቆረስ፤ ንፁህ ዜጋ ወንጀለኛ ተብሎ ቢፈረድበት፤ ሌላም ሌላም፤ ሁሉም ለኔ ጉዳዮቼ አይደሉም። ከኔ የሚጠበቀው መንግስት የሚፈልገውን እየሰራሁና እያስተጋባሁ ኑር እስከተባልኩ ድረስ መኖር ብቻ ነው።” እየሰማሁ ያለሁት ጉዳይ በጣም ግራ ስላጋባኝ፤ በአንድ በኩል የሰው ልጅ እንዴት በእንደዚህ የተሳሰ ሁኔታ መኖር ይችላል!? መለስ እልና ደግሞ ጓደኛዬን ድሮ ሳውቀው አደለም የማያምንበትን፤ አምኖ የተቀበለውን እንኳ በተገቢው መፈፀም እንደሚያጨናንቀው ነበር፤ አሁን ታዲያ ምን ነክቶት ይሆን!? ሌሎች ብዙ ጥያቄዎችን በውስጤ እያሰላሰልኩ፤ የራሴ አለም ውስጥ ሳላስበው ሰጥሜ አዳምጠው ነበር። እርሱ ግን ንግግሩን ቀጥሏል፤ “መንግስት ኢኮኖሚው በሁለትም በሶትም ዲጂት አደገ ካለ፤ እኔም ያንን አስተጋባለሁ፤ ቁጥር የኔ ጉዳይ አይደለም።”

በዝምታ አንገቱን አቀርቅሮ ለጥቂት ሴኮንዶች ጨዋታውን ሲያቋርጥብኝ፤ ያልሆኑ ጥያቄዎችን አምጥቼ ወዳጄን ያስከፋሁት ስለመሰለኝ፤ ነገሩን ወደ ሌላ ጨዋታ አቃልዬ ለማስቀየር በማሰብ፤ እሺ እና ቤተሰብ እንዴት ነው ባክህ!? አልኩኝ። እርሱ ግን ቀና ብሎ አይቶኝ ጨዋታውን ቀጠለ፤ “ንግድ ውስጥ እንዳለሁ ነግሬሃለሁ፤ አይደል!?” አለኝ። ደንገጥ ብዬ፤ በፍጥነት “አዎን ነግረኸኝ ነበር” አልኩ። “ታውቃለህ!?” አለኝ፤ “አንድ የመንግስት የበላይ ባለስልጣን ወይንም ወዳጁ፤ በማንኛውም ሰአት የኔ ቢዝነስን ሼር ሆልደር ልሁን ወይም ልግዛህ ካለኝ በደስታ እቀበላለሁ። ባይገርምህ እስካሁን ስንት የንግድ ድርጅቶች ቀያይሬአለሁ መሰለህ!” “ባክህ ተወኝ ብዙ አታሶራኝ እኔ ተመችቶኛል። ይልቁንስ የሚያሳዝኑኝ ድርጅታቸው ሲቀማ፤ እንደ አዲስ መጀሩ ታክቷቸው ነገር አለሙን እርግፍ አርገው የሚተዉት ሰዎች ናቸው።” “እኔ እንኳ በአዲስ መጀመር ምንም አይመስለኝም፤ ከንግዲህ እንዳትሰራ ካላሉኝ በስተቀር።” አለ ፈገግ ብሎ እየተመለከተኝ።

“አሁን ግልፅ ሆነልክ!?” ጠየቀኝ፤ ነገር ግን መልሴን ሳይጠብቅ ንግግሩን ቀጠለ፤ “ስለዚህ ህጉ ላጲስ አለው ያልኩህ ለዚህ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ወንጀል እንደ እኔ አይነቱን ልማታዊ ዜጋ በህግ አያስጠይቀውም፤ አያስቀጣውምም።” “ለነገሩ ባለስልጣናቱንም አያስጠይቅም፤ ከዋናዎቹ ጋር እስካልተቃረኑ ድረስ።” “እስኪ በየ እስር ቤቱ የታጐረውን ዜጋ አስብ!!!? እውን እንደሚባለው ወንጀል ፈፅሞ ይመስልካል!?” “የትኞቹ ጋዜጠኞች ናቸው ወደ እስር ተወርውረው የተረሱት!?” “ፖለቲከኞቹስ ቢሆኑ!? ሁሉም የሚታሰሩ ይመስልሃል!?” “ስንቱ ከስራ ተባሮ ቦዘኔ ደሓ ሁኖ የቀረው ስራውን በአግባቡ ስለማይሰራ ይመስልሃል!?”

“ስለዚህ እመነኝ፤ እኔ ለልማታዊው መንግስታችን የምመች ልማታዊ ዜጋ ሆኛለሁ።” “መንግስታችን እንደኔ አይነቶቹ ዜጐች ከሌሉ ለህልውናው ስለሚሰጋ ይንከባከበናል። ስለዚህ አትጨነቅ።” “በርግጥ ይህን እንዳጫወትኩህ ከሰሙ ነገ ወደ እስር ቤት እንደምጓዝ አትጠራጠር። ለነገሩ አንተ ካልነገርካቸው በስተቀር የዛሬው ጨዋታችንን አይሰሙትም። ምክንያቱም አይከታተሉኝማ፤ አውቃለሁ።” “እነርሱ የሚከታተሉህ ‘ልማታዊ ዜጋ’ ካልሆንክ ብቻ ነው።”አለና ቀና ብሎ እያየኝ “አሁን ገባህ!? መንግስታችን የሚያወጣቸው ህጐችና መመሪያዎች ከጐናቸው ላጲስ አሏቸው።” “በላጲሱ ማጥፋት የሚችለው ግን መንግስታችን ብቻ ነው።” “እንዲያጠፋልክ የምታዘው ደግሞ አንተ ነህ፤ ‘ልማታዊ ዜጋ’ በመሆን።” “ይሄው ነው ወዳጄ።” አለኝ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!

Comment

The post ልማታዊው ጓደኛዬ – ከዋስይሁን ተስፋዬ appeared first on Zehabesha Amharic.

አስቂኙ የአቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ቃለ መጠይቅ! –ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

$
0
0

amsaluየኢሳት ራዲዮና ቴሌቪዥን (ነጋሪተ ወግና ምርዓየ ኩነት) ጋዜጠኞች ከሕዝባዊ ግንባር መሪ አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ጋር ያደረጉትን ቃለ መጠይቅ ተከታተልነው፡፡ ያው አስቀድሜ እንደገመትኩት በአሮጌው ድሪቶ ላይ አሮጌ ጨርቅ ድረታና እብለት ክህደት እንጅ የነበረውን አሮጌውንና ያላዋጣውን በመተው በአዲስና በተመከረ በተማረ ልብ አዲስ ሐሳብ አዲስ መንገድ ለመቀየስ አልተፈለገም፡፡ የሚጠበቀውና አስፈላጊው ግን ይሄኛው ነበር፡፡ ለነገሩ ከአንባገነን ሥርዓት ባለሥልጣናት ይሄ የሚጠበቅ አይደለም እንደነዚህ ዓይነት ሰዎች እንኳን በአንድ ሰው ዕድሜ ሽህ ዓመታት የመኖር ዕድል ቢሰጣቸው እንኳን እስከ መጨረሻዋ ደቂቃ ድረስ ሱሪያቸውን በአንገት ለማጥለቅ እንደታገሉ ያልፋሉ እንጅ አይ ሐሳቤ መንገዴ ይሄንን ያህል ዘመን ብታገልም ሊሠራ አልቻለም፡፡ ሊሠራ ያልቻለበትም የራሱ ምክንያት ችግር ስላለበት ሳይሆን አይቀርምና እስኪ ወይ ለሌላው ዕድሉን ልስጥ ወይ አስተሳሰቤን ቀየር ላድረገው አይሉም፡፡ ተፈጥሯቸው አይፈቅድላቸውምና ግትሮች ናቸው፡፡ ሰውየውን አላያቹህትም?  ጓደኞቹን ሰጥ ለበጥ አድርጎ እንቢ ያለውን አጥፍቶ ፈላጭ ቆራጭ ሆኖ ብቻውን ገኖ መግዛት በመቻሉ የሚነበብበትን የእርካታ ስሜት አልታያቹህትም? የተሳካላት የሞላላት ሀገር መሪ እንጅ በተወሳሰበ ችግር ውስጥ ያለች ከዕለት ወደ ዕለት እየተመሰቃቀለች የሕዝቧ ኑሮም እየከፋ ያለች ሀገር መሪ ይመስል ነበር?

እናም ከቃለ ምልልሱ አንድም እንኳን ፍሬ አላገኘሁበትም፡፡ እንዲህ ይባላል እንዲህ ይባላል ስለሚባሉ ነገሮች ተወራ እንጅ በፖለቲካዊ (በእምነተ አሥተዳደራዊ) ጉዳዮች ላይ ግብራዊ (ቴክኒካል) የሆኑ ጥያቄዎች ለምሳሌ በአሰብ ወደብ ዙሪያ ያለውና የመሳሰሉ ዋና ዋና ጉዳዮች ስላልተዳሰሱበት በግሌ ቅር ብሎኛል፡፡ ሲጀመር ቃለ መጠይቁ የቃለ መጠይቅ አሠራርናንና ሒደትን የተከተለ አይደለም፡፡ ጋዜጠኞቹ ትግርኛን ባለማወቃቸው ጥያቄዎችን መጠየቃቸውን እንጅ የጠየቁት ጥያቄ በአግባቡ ስለመመለሱና አለመመለሱ ማረጋገጥ እንዳይችሉ አድርጓል፡፡ ሰውየው ማውራት የምፈልገው በትግርኛ ነው ካሉ መብታቸው ነው ነገር ግን የሚመልሱትን ለጋዜጠኞቹ የሚተረጉም አስተርጓሚ በመሀል መኖር ነበረበት፡፡ ይሄ ባልሆነበት ሁኔታ እንዴት ቃለ ምልልሱን ለማድረግ እንደፈቀዱ አልገባኝም፡፡ አስተርጓሚ ከሌለም ጠያቂዎቹና ተጠያቂው በጋራ በሚያውቁት ቋንቋ መደረግ ነበረበት፡፡ ወደ ኋላ ላይ አቶ ኢሳይያስ ከትግርኛ ወደ እንግሊዝኛ በመሔዳቸው ለጋዜጠኞቹ ሰውየው የሚሉትን ነገር ምንነት ለመረዳት የተሻለ ዕድል የሰጣቸው ቢሆንም የተጠቀሙበት ግን አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም ጥያቄው ይጠየቃል ሰውየው የፈለገውን ሰዓት ያህል ወስዶ ሌላ ነገር ሲቀበጣጥር ቆይቶ ሲጨርስ ሌላ ጥያቄ ደሞ ይጠይቃሉ እንጅ ከጭብጥና ከነጥቡ ውጭ ሲወጣባቸው መመለስ፣ በአግባቡ ያልተመለሰውን እንዲመልስ ማድረግ፣ በዋሸባቸው ወይም በካዳቸው ባበለባቸው ጉዳዮች መሞገት የተባሉ የጋዜጠኛ ሥራዎች ሲሠሩ ባለማየቴ ከፍቶኛል፡፡ ኢሳት ኢሳትን እንጅ ኢቴቪን መሆን አልነበረበትን፡፡ በእርግጥ እነዚህ የኢሳት ጋዜጠኞች ከብቃት ማነስ ሳይሆን ከአቶ ኢሳይያስ ጋራ በገለጽኩት መልኩ ቃለ መጠይቅ ማድረግ እንደ ሌሎቹ ሁሉ እነሱንም እንዳይመለሱ አድርጎ ወኅኒ ሊያስወርዳቸውም ይችላልና ይሄንን ከመፍራት ሳያደርጉት ቀርተው ከሆነ ልንረዳላቸው ይገባል፡፡ አስቀድሞ እንዲህ ዓይነት ሥጋት ከነበራቸው ደግሞ ቃለመጠይቁን ማድረጉ አስፈላጊ አልነበረም፡፡

አንዴ ብቻ አቶ ኢሳይያስ 90ሽህ የደርግ ወታደሮችና ባለሥልጣናት ከባሕረምድር ተሸንፈው በሚወጡበት ወቅት “እንኳን የበቀል እርምጃ ስድብ እንኳን የተናገራቸው አንድ ሰው እንኳን የለም” በማለት የሰውየውን የውሸታምነት ደረጃ የሚያሳይ አስቂኝ ቃል በተናገሩ ጊዜ ፋሲል ምንም እንኳን ሰውየው ተናግረው ጨርሰው ሌላ ጥያቄ ለመቀበል በተዘጋጁበት ሰዓት ቢሆንም “እዚህ ላይ ይቅርታ ላቋርጥዎት” በማለት እነዚህ አቶ ኢሳይያስ 90 ሽህ ናቸው ያሏቸው የደርግ ወታደሮችና ባለሥልጣናት ጥርሳቸውን ሳይቀር እንዲወልቅ እንደተደረገ የእጅ ሰዓት የአንገት ሀብልና ሌሎች ንብረቶች ሁሉ እንደተዘረፉ በታሪክ እንደሰማ አሁን እሳቸው ያሉት ደግሞ ከዚህጋር እንደተለየበት ጠይቋቸው ነበር፡፡ ምንም እንኳን አቶ ኢሳይያስ ለዚህ ጥያቄ ምን እንደመለሱ ኢሳት ባያስደምጠንም ቅሉ፡፡ ለመሆኑ የዚህን ጥያቄ መልስ እንዳንሰማው የተደረገው ለምንድን ነው?

አቶ ኢሳይያስ የገረሙኝ ነገር ቢኖር ፖለቲካዊ ጉዳዮችንስ እሽ መደበቅ የሚፈልጉት ጉዳይ ስለሚኖር ለመሸሽ ሌላ ሌላ ነገር ቀበጣጥረው አለፉ እንበል እሳቸው እኮ ቢናገሩት አድማጩን ምንም የማይጠቅመውንና የሚያውቀውን ጉዳይ ሁሉ እኮ ነበር ሊናገሩ ያልቻሉት፡፡ ለምሳሌ ስለ ራሳቸው ስለ ልጆቻቸው ተጠየቁና ሲመልሱ ይሄም ቁም ነገር ሆኖባቸው ልጆቻቸው ማን ማን እንደሚባሉና ስንት እንደሆኑ ምን እንደተማሩ አንድም ነገር ሳይናገሩ ተፈላሰፍኩ አሉና “ዘለው የባለ ሥልጣን ልጆች ስለሆኑ ከሌላው በተለየ ሊታዩ አይገባም እነሱም ሰው ናቸው ሁለት ዐይኖች እንጅ አራት ዐይኖች የላቸውም ሁለት ጆሮዎች እንጅ አራት ጆሮዎች የላቸውም ሁለት እግር እንጅ ሁለት እጅ እንጅ አንድ አፍንጫ እንጅ አንድ ምንትስ ሁለት ቅብርጥስ” እያሉ በመዛዛት ስንት ነገር ሊሠራበት የሚችለውን ወርቃማ ጊዜ እንዲያው በከንቱ አባከኑብን፡፡ ከሰው ልጅ ከተወለዱ ሁለት አንድ እያሉ የዘረዘሯቸውን የሰውነት አካላት እንደሚይዙ ማን ያጣዋል ብለው ነው አቶ ኢሳይያስ? መጀመሪያ እነማን እንደሆኑ መች አስተዋወቁንና? ስለነሱ ልናወራ የምንችለው መጀመሪያ ልጆች እንዳሏቸው ሲያሳውቁን አልነበረም እንዴ? ያሉት ነገር እውነት በሆነ በእውነት ከፍልስፍና በቆጠርኩልዎት ነበር እርስዎንም ለሕዝብ እንደሚያስብ ቅን አሳቢ ቡቡ መሪ በቆጠርኩዎት ነበር፡፡ አቶ ኢሳይያስ እንዲያው ግን ሰው ይታዘበኛል የሚባል ኅሊናም የለዎት? አሁን ማን ይሙትና እርስዎን ጨምሮ ልጆችዎ የእርስዎ ልጆች ኑሮ ከተራው ዜጋ ኑሮ ምንም ያልተለየ ነው? እርስዎና የእርስዎ ልጆች አብዛኛውን ጊዜ የሚበላውን አጥቶ በቀን አንዴ እንደሚበላው ባስ ሲልም ጦም እንደሚያድረው እንደአብዛኛው የገጠር ሕዝብዎና እንደከፊሉ የከተማ ሕዝብዎ ጦም አድራቹህ ወይም በቀን አንዴ ብቻ ተመግባቹህ ታውቃላቹህ? የምትቀይሩት ልብስ አጥታቹህ በአንድ ልብስ ላይ ተጣብቃቹህ ታውቃላቹህ? መኝታቹህን ትኋን ቁንጫና ቅማል ይዘልበታል? ባለው ከፍተኛ የውኃ ችግር እንደሌላው ሁሉ ልብሶቻቹህ ሳይታጠቡ ንጽሕናቹህ ሳይጠበቅ በክታቹህ ትሰነብታላቹህ? የማይመስል ነገር እየቀባጠሩ ሲወሸክቱ ምን ያህል ግብዝና አስመሳይ አታላይ መሆንዎ ነው ቁልጭ ብሎ የታየኝ፡፡

የጥያቄዎችን ጭብጥና ነጥብ ሳይጠብቁ የሰውነት አካላትን ሁሉ አንድ ሁለት እያሉ እርባና የሌለውን ዝባዝንኬና የባጥ የቆጡን ወሬ እየቀበጣጠሩ ረጅም ሰዓት ማውራት ችሎታና ብቃት መስሎዎት ነው አቶ ኢሳይያስ? ለዛ ነው እንዴ “በዚህ ጉዳይ ላይ ለሰዓታት ላወራ እችላለሁ!” ሲሉ ደረትዎን ነፍተው የተናገሩት? አየ አቶ ኢሳይያስ! እንደ ማን የሆኑ መስሎዎት ነው? እንደ ኩባው ፊደል ካስትሮ? ነው ወይስ እንደ ሊቢያው ጋዳፊ? እንዲህ ጊዜ ወርቅ በሆነበት ከወርቅም አልማዝ ከአልማዝም ዩራኒየም በሆነበት ዘመን በዝባዝንኬ ወሬ እርስዎም ሥራ ፈተው እኛንም ቁምነገር ያወራሉ መስሎን ሥራ አስፈትተው ይሆናል ብለው ነው? ነው ወይስ “ጊዜ ወርቅ ነው” የሚለው ብሂል ገና እርስዎ ላይ አልደረሰም? አዎ በሥራዎ በአስተሳሰብዎ ሁሉ እያየነው አይደል? አሁን ሌላ ጊዜ አቶ ኢሳይያስ ቃለ መጠይቅ አላቸው ቢባል ማን ነው ቁጭ ብሎ የሚሰማልዎት? አየ አቶ ኢሳይያስ! ለሌላው ጊዜ ግን ሲጠየቁ በነጥቡ ላይ ብቻ አተኩረው ከጭብጥ ሳይወጡ ጥያቄውን መመለስ ነው እንጅ ያልተጠየቁትን የሰውነት አካላት በመዘርዘር የሰው ውድ ጊዜ አያባክኑ እሽ? መመለስ የማይፈልጉት ጥያቄ ካጋጠመዎት ደግሞ እንደሌሎቹ መዝለል ነው እንጅ የማይረባ ዝባዝንኬ መቀበጣጠር ያስገምትዎታል፡፡

አቶ ኢሳይያስ በጣም አስገራሚ ሰው ነዎት፡፡ ፍልስፍናው እንደሱ አይደለም፡፡ ቅዠት በሆነና የትም ቦታ ባልታየ ሊታይ ሊተገበር ባልቻለ የኮሚውኒዝምና (መደባዊ ያልሆነ ሥርዓተ ማኅበር) የሶሻሊዝም (የኅብረተሰባዊነት) ፍንስፍና እየዳከሩ ጊዜዎን በከንቱ ባያቃጥሉ ሕዝቡንም ባያደክሙ ባያንገላቱት መልካም ነው፡፡ ምክንያቱም ይሄ ፍልስፍና ሲበዛ ተምኔታዊ (Ideal) በመሆኑና ማንም ሀገር በትክክል ሊተገብረው ስላልቻለ ሊተገበርም ስለማይቻል፡፡ ሲሰሙት ደስ ይላል አማላይም ነው ተግባራዊ ማድረግ ግን ፈጽሞ የሚቻል አይደለም፡፡ እዚህ ላይ ትንሽ የጭንቅላት እጥበት (brain wash) ላደርግዎት እፈልጋለሁ፡፡ ይሄውልዎት አቶ ኢሳይያስ እያንዳንዱ ሰው የልፋቱን ያህል ማግኘት ካልቻለና ጠንካራውም ደካማውም ምሁሩም መሀይሙም እኩልና ተመሳሳይ የኑሮ ደረጃ እንዲኖረው ከተደረገ ውጤቱ ሰውን ከአቅም በታች እንዲሠራ እንዲለግም ያደርጉታል በዚህም ሀገር ትጎዳለች እንጅ እንዲተጋ፣ አቅሙን አሟጦ እንዲፈጋ፣ እራሱን በሥራ እንዲጠምድ፣ ለጥራት ትኩረት እንዲሰጥ ሊያደርጉት አይችሉም ንግድን ጨምሮ ሌሎች እንቅስቃሴዎች ሁሉ አይነቃቁም፣ ኑሮ ፉክክር የሌለበትና አሰልች ይሆናል ፈጠራ ግኝትና ፍልሰፋን የመሰሉ የንቁ ጭንቅላት ፍሬዎችማ ጨርሶ የሚታሰቡ አይሆንም፡፡ ሰው አዳዲስ ነገር ሊፈጥር ሊያገኝ ሊፈለስፍ የሚችለው የሚበረታታው የድካሙን የልፋቱን የጥረቱን ያህል ሲከፈለው ዕውቅናና አክብሮት ሲቸረው እንጅ ያንን ያህል ደክሞ ለፍቶ ጥሮና ግሮ ከተራው ዜጋ ጋር በተመሳሳይ የኑሮ ደረጃ እንዲኖር ሲደረግ አይደለም፡፡ ይሄ የሥራ መነቃቃት ስሜትን ይገላል፡፡ ለብርቱው ለታታሪው ለጠንካራው የየጥረቱን ያህል ዳጎስ ዳጎስ ያለ ክፍያ ሲከፈለው ግን መነቃቃት ይፈጠራል፡፡

አንድ ቀላል ምሳሌ ልስጥዎት አቶ ኢሳይያስ፡- በአንድ ክፍል ውስጥ ተማሪዎች ብቃታቸውና ችሎታቸው የተለያየ ሆኖ እያለ እኩል ነጥብ ልስጥ ይላሉ እንዴ? ሁሉም ተማሪዎች እኩል የመቀበልና የመረዳት አቅም ችሎታ ሊኖራቸው አይችልምና ወይም አንደኛው ከሌላኛው ሊጎብዝና ሊሰንፍ ይችላልና እኩል ነጥብ ልንሰጥ አንችልም አይገባምም ካደረግነውም አሠራራችን ፍትሐዊና አመክንዮአዊ አይሆንም፡፡ የተፈጥሮ ጉዳይ ነውና ሁሉንም እኩል ማጎበዝ እኩል እንዲያስቡ ማድረግም አይቻልም፡፡ ልናደርግ የምንችለው ሁኔታዎችን በማመቻቸትና በመርዳት የሚሰንፍ ሰው እንዳይኖር ምርጥ ብቃቱን ችሎታውን እንዲጠቀም ማድረግ፡፡ እንዲህ አድርገን ከረዳናቸው በኋላ ችሎታቸው ብቃታቸው በፈቀደላቸው መጠን የሚያመጡትን ውጤት ግን የየችሎታቸውንና ውጤታቸውን ያህል ነው ሊሆን የሚገባው፡፡ ይሄ ካልሆነና ለሁሉም እኩል ነጥብ የሚሰጥ ከሆነ ግን የሚጎብዝ ተማሪ ሊወጣ አይችልም፡፡ ምን አለፋውና? በሥራም ዘርፍ ያለው ነገር እንዲሁ ነው፡፡ ስለሆነም ጠንክሮ በርትቶ የሠራ ሀብታም የሚሆንበት የተሰጠውን ዕድልና ድጋፍ መጠቀም ሳይችል ቀርቶ የወደቀው ደግሞ ደህይቶ በድህነት የሚቀጣበት ሁኔታ ክፍት መሆን አለበት፡፡ ባለፀጋው በድካሙ በጥረቱ በልፋቱ አግኝቷልና የድካም ፍሬውንም እንዲበላ ሊፈቀድለት ይገባል፡፡ ሰው የሚደኸየው በስንፍናው ብቻ አይደለምና ባለጸጋው በሰብአዊነት በራሱ ፈቃድ ድሆችን መርዳት ከፈለገ ግን የፈቀደውን ያህል ያለውን ማካፈል መብቱ ነው፡፡ የሞራል (የቅስም) ግዴታም አለበት፡፡ በግድ ግን ያለህን አምጣ ከሌላው የተለየ የላቀ ኑሮ ልትኖር አትችልም ሊባል አይገባም፡፡ በዚህ ዓይነት አሥተዳደር ሀገር ልትገነባ ዜጎች ሊለወጡ አይችሉም፡፡

የሀገራት መሪዎች ሊጠነቀቁ የሚገባው ነገር ቢኖር ለሁሉም ዜጋ ሠርቶ ሊለወጥ ሊበለጽግ የሚችልበት እኩል ዕድል የመኖሩን ጉዳይና ሕግ ከፈቀደው መንገድ ውጪ ሊበለጸግ የሚቻልበትን ሙስናን የመሰለ አግባብ ያልሆነና ሕገ ወጥ አሠራር ኖሮ ዜጎች ሠርተው መለወጥ የሚችሉበትን ዕድል አጥተው ጥቂቶች ወንጀለኞች ብቻ ደግሞ የሚበለጽጉበት ሁኔታ እንዳይፈጠር እንጅ በነጻና ፍትሐዊ ፉክክር የጠነከሩት የበረቱት ሠርተው ማግኘት መለወጥ የሚችሉት ዜጎች መኖራቸው አይደደለም ሊያሳስባቸው የሚገባው፡፡ ይሄማ ሥጋት ነው ሊሆን የሚችለው የአንባ ገነን መሪዎች ሥጋት፡፡ በበረቱ በበለጸጉ በነቁ በበቁ ሰዎች እንዋጣለን ጥቅማችን ይጎዳል ሥልጣናችንን ሁሉ ልናጣ እንችላለን የሚል የሀገርን ጥቅም ሳይሆን የግል ጥቅማቸውን ማዕከል ያደረገ ሥጋት፡፡ ሲመስለኝ የእርስዎም ሥጋት ይሔው ነው ምክንያቱም ከላይ እንደገለጽኩት እርስዎ የተናገሩትን እርስዎም ሆኑ ልጆችዎ አትኖሩትምና ነው፡፡ ጉርድ ሸሚዝና ክፍት ጫማ አድርገው መታየትዎ ወደ ኋላ ላይ ተስቶዎት እውነቷን እንደተናገሩት ቀለል ያለ የኑሮ ዘይቤ ስለሚወዱ እንጅ መግቢያዎ ላይ ለማወናበድ ይታሰብልኛል ብለው እንደገመቱትና እንደተናገሩት ከተራው ሕዝብ የተለየ ኑሮ እንዲኖርዎት የማይፈልጉ ስለሆኑ አይደለም፡፡ ባሰኘዎት ጊዜና ቦታ ደግሞ እንዴት እንደሚዘንጡ በሚገባ እናውቃለንና፡፡ በእርግጥ አንዳንድ የዋሀንን ሊያታልሉ ይችሉ ይሆናል የሆነ ሆኖ ግን እውነት ያልሆነና የማስመሰል ነገር መሠረታዊ የሆነ ለውጥ አያመጣምና እንዲህ ዓይነቱን ነገር ቁም ነገሬ ብለው ባይይዙት መልካም ነው፡፡ እርስዎንም ማንንም አይጠቅምምና፡፡

በተመሳሳይ ስለ የትጥቅ ትግል ለማድረግ እናንተጋ ስላሉት የተቃውሞ ኃይሎች “ሸአቢያ አንድ እንዳይሆኑ ያደርጋል፣ በዘር ወይም በብሔር እየከፋፈለ በማደራጀት የተለያየ ዓላማ ያላቸውን የተለያዩ ብሔር ተኮር የፖለቲካ ድርጅቶችን ይፈጥራል ይባላልና ለዚህ ምላሽዎ ምንድን ነው?” ተብለው ለተጠየቁት በመቀበጣጠር “ኦነግን፣ ኢሕአፓን፣ ምንትስን እያሉ እኛ ከመመሥረታችን በፊት የተመሠረቱ በመሆናቸው እኛ ልናደራጃቸው አንችልም” አሉ ታደራጃላቹህ የተባላቹህት መቸ እነሱን ሆነና? በደንብ ካላዳመጡ ጥያቄው እንዲብራራልዎት መጠየቅ ነው እነማንን ማለትህ ነው ቢሉ ይዘረዘርልዎት ነበር እነሱንስ ቢሆን እንዳይግባቡና አንድነት እንዳይፈጥሩ እንደሚያደርጉ የማናውቅ ይመስልዎታል? አዳዲሶቹን በሀገሪቱ ያለው የወያኔ የዘር ፖለቲካ የፈጠራቸው እንጅ እኛ አልፈጠርናቸውም አሉ “ለማያውቅሽ ታጠኝ” አለ ያገሬ ሰው እነ መለስ ሕገመንግሥቱን ሲያሳዩኝ የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘር የሚከፋፍልና የማይጠቅም ነው ብለው ወያኔን የመከሩ ሰው ከሆኑ በወያኔ የዘር ፖለቲካ ተሳስተው በሀገርዎ የተደራጁ ወገኖችን መክረውና እንደማይጠቅም አስረድተው በአንድ እንዲደራጁ ማድረግ ምን ነው ተሳነውትሳ ታዲያ አቶ ኢሳይያስ?

እኔማ የሚጠየቁት ሌላ የሚመልሱት ሌላ ማሞ ሌላ መታወቂያው ሌላ ፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ አራንባና ቆቦ እየሆነ ሲያስቸግረኝ ይቅርታ ይደረግልኝና ሰውየው ጤነኛ መሆናቸውን ሁሉ ለመጠራጠር ነው የተገደድኩት፡፡ ዝም ብሎ ይቀዳል ሰውየው እውነት ተናገረ ውሸት የሚለውን ለጊዜው እንተወውና እንደ ፖለቲከኛ እንኳን ምን ብል ይታመንልኛል? ምንስ ብል አይታመንልኝም? የሚለውን ነገር ጨርሶ መለየት የሚችል ሰው ሆኖ አላገኘሁትም፡፡ ጤነኛ ሰው እኮ ሲጠይቁት ምን እንደጠየቁት አውቆ ተረድቶ የተጠየቀውን በአግባቡ ሲመልስ እንጅ የተጠየቀውን ትቶ ጨርሶ የማይገናኝ ነገር ከቀበጣጠረ እንዴት ነው ጤነኛ ነው ልንል የምንችለው? ባጠቃላይ ሰውየው አውርቶ የሄደው ሊያወራው ሲዘጋጅበት የሰነበተውንና የሸመደደውን ነገር ነው አውርቶ የሄደው ጥያቄ የተባሉት ባይሰነዘሩና ቪዲዮ ካሜራ (መቅረጸ ትዕይንት) ደቅነው ቢተውለት ራሱ ይሄንኑ ራሱን አንዳችም ሳይቀንስ ሳይጨምር ሊያወራላቸው ይችል ነበር፡፡

ሲያወራው የነበረው በጠቅላላ ሐሰት ነበር፡፡ ምን እንደሚዋሽም አላወቀም ለምሳሌ እነዚያ 90 ሽህ የተባሉ የደርግ ወታደሮችና ባለሥልጣናት ሁሉም ባይሆኑ በአብዛኛው በሕይዎት ባሉበትና የተፈጸመባቸውን ግፍ በሚገባ ሊናገሩ ሊመሰክሩ ሊያረጋግጡ በሚችሉበት ሁኔታ ሽምጥጥ አድርጎ ክዶ “እንኳን የበቀል እርምጃ ስድብ እንኳን የተናገራቸው አንድ ሰው የለም” ባለበት ሁኔታ ሰውየው ምን እንደሚያስተባብል ምን እንደማያስተባብል ለይቶ ያውቃል ማለት እንዴት ነው የሚቻለው? አቶ ኢሳይያስ ያ የሠሩት ግፍ ከባድነት ታወቃቸው እንዴ? ነው ወይስ ካደረሱባቸውም ግፍ በላይ ሳይፈጇቸው በመልቀቃቸው ቆጫቸው?

ለነገሩ ሰውየው ይሄ ጠፍቶት አይመስለኝም ሰውየው ከገመትኩት በላይ የተዋጣለት አሽሙረኛ ሆኖ ነው ያገኘሁት፡፡ አቶ ኢሳይያስ በወቅቱ 90 ሽህ ናቸው ባሏቸው የደርግ ወታደሮችና ባለሥልጣናት  ላይ ምን ምን ዓይነት ግፍ እንደተፈጸመባቸው በምን መልኩ ሰብአዊ ክብራቸው ተዋርዶና ንብረታቸው ተዘርፎ የወርቅ ጌጣጌጥ እንደ ቀለበትና ሀብል ደብቃቹሀል እየተባሉ እያስጎነበሱ ፍንጢጣቸው ሳይቀር እየተፈተሸ ከለበሱት ልብስ አቅም እንኳን እያስወለቁ ድሪቶ እያለበሱ ወይም እርቃናቸውን እየሆኑ እንዲወጡ እንደተደረጉ አቶ ኢሳይያስ አትተውት ወይም ሳያውቁ ቀርተው አይደለም፡፡ ነገር ግን የደርግ ወታደሮችና ባለሥልጣናት የነበሩት በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ሆነው አሁንም ድረስ በተቃውሞው ጎራ ተሰልፈው ሀገራቸውን ለማገልገል በሚያደርጉት ጥረት ሸአቢያ ጥቅሙ እየተጎዳበት ማንነቱ እየተጋለጠበትና በ1990ዓ.ም. ላይ በተደረገው ጦርነትም ጉልህ ሚና መጫወታቸው እነዚህን ወገኖች በሕይዎታቸው የማይረሱትን ክፉ የሕይዎት አጋጣሚ እንዲያስታውሱት አድረገው አቁስለው ሲያበቁ እንደገና ደሞ ያኔ ከተፈጸመባቸው ግፍ በላይ የተፈጸመባቸውን ግፍ ፈጽሞ እንዳልተፈጸመባቸው ተደርጎ ተሸምጥጦ በመካዱ እንደገና እንዲቆስሉ እንዲያሩ እንዲበግኑ ማድረግ ፈልጎ ነው ሰውየው ሀገር ያወቀውን ፀሐይ የሞቀውን የአደባባይ ምሥጢር ሸምጥጦ ለመካድ የሞከረው፡፡

እናም ብቻ በእነዚህ በእነዚህ ምክንያቶች ይሄ ቃለ መጠይቅ እርባና ቢስ የሚነሣ ነገር አንድ እንኳ የሌለው ነው የሆነብኝ፡፡ ነገር ግን እንዲያው አንዳንድ የገረሙኝንና የሰውየውን የዋህነት አጉልተው ያሳዩኝን አንዳንድ ነገሮች ሰውየውንም ሀገራችንንም ሕዝባችንንም እጅግ የሚጎዱ ሆነው ስላገኘኋቸው በእነሱ ጉዳዮች ላይ ማውራት ግድ ብሎኛል፡፡

አንደኛው አቶ ኢሳይያስ ፈርጠም ብለው ሲናገሩ ምን አሉ? “የሁለቱም ሀገሮች ግንኙነት 1997 (1989ዓም.) በፊት ወደ ነበረው ሰላማዊ ግንኙነት መመለስ አለበት” አሉ፡፡ ይህች አነጋገር እንዲህ ቀላል አነጋገር እንዳትመስላቹህ፡፡ አቶ ኢሳይያስ እንዲህ ሲሉ ምን ማለታቸው እንደሆነ ለብዙዎቻችን ግልጽ እንዳልሆነ እገምታለሁ፡፡ አቶ ኢሳይያስ እንዲህ ሲሉ ምን ማለታቸው ነው? እንደምታስታውሱት ወያኔና ሸአቢያ ግፍን የሚመለከተው የመድኃኔዓለም እጅ ገብቶበት ግንኙነታቸው ሻክሮ ከመጣላታቸው በፊት ሸአቢያ በሀገራችን የኢኮኖሚ (የምጣኔ ሀብት) እንቅስቃሴ ከፍተኛ ጫና ይፈጥር ነበር፡፡ አንድ ምሳሌ ብሰጥ ኤርትራ አንድ እንኳን የቡና ችግኝ የማይገኝባት ሆና እያለ በዓለም ካሉ ታዋቂ ቡና ላኪ ሀገራት ውስጥ አንዷ ሆና የተመዘገበችበት ሁኔታ ተፈጥሮ ነበር፡፡ ቡናችንን ብቻ ይደለም እንደ ሰሊጥና ጥጥም የመሳሰሉ የግብርና ምርቶቻችንንም እንጅ፡፡ በዚያ ወቅት ሸአቢያ ያለ አንዳች ከልካይ በሀገራች ገበያ ላይ እንደፈለገ እየዋኘ ምርቶችን እየጫነ እየወሰደ ነበር ለውጭ ገበያ ያቀርብ የነበረው፡፡ አቶ ኢሳይያስ 1989ዓም. በፊት ወደ ነበረው ግንኙነት መመለስ አለበት ሲሉ አሁንም እንደያኔው ገብቸ የምዘርፍበት ሁኔታ መፈጠር አለበት ማለታቸው ነው፡፡ ለጦርነቱ መፈጠር መንስኤ የሆነውም ይሄው ነው ወያኔም በመንቃቱና ሸአቢያ የሚያገኘውን ጥቅም በንግድ ድርጅቶቹ በኩል ለራሱ ሊበላ ስለፈለገና ሸአቢያን በመከልከሉ በተፈጠረው ውዝግብ ሸአቢያ እነዚህንና ሌሎች ምርቶችንም ከሀገራችን እየዘረፈ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የማይችልበት ሁኔታ መፈጠሩ ነው የጦርነቱ መንስኤ፡፡ ባድመ ሰበብ እንጅ ትክክለኛው መንስኤ እሱ አልነበረም፡፡ እናም አቶ ኢሳይያስ ያ ወርቃማ ዘመናቸው ዛሬም ድረስ በዐይናቸው እንደዞረ አለ ደግመው ሊያገኙትም እጅግ ይመኛሉ ይቋምጣሉም፡፡

እኔ ከዚህ ቃለ መጠይቅ የተረዳሁት ነገር ቢኖር ሸአቢያ ከሚገመተው በላይ አደገኛ የሆነ የጥገኝነት ተፈጥሮና አስተሳሰብ እንዳለበት ነው፡፡ ከዚህ የተነሣ ነው አቶ ኢሳይያስ “የኛ ፍላጎት የነበረው ከኢትዮጵያ ጋር በአንድ ገንዘብ፣ በአንድ የቁጥጥር (monitory) እና የመንግሥት ገቢ (fiscal) መመሪያ (policy) እንድንተዳደር ነበር” አሉ፡፡ ይታያቹህ! አቶ ኢሳይያስ ለመሆኑ ተገንጥለናል ራሳችንን የቻልን ሉዓላዊ ሀገር ሆነናል ካሉ በኋላ እንዴትና ለምንድን ነው እሱ በአንድ ገንዘብ፣ በአንድ የቁጥጥር (monitory) እና የባጀት (fiscal) መመሪያ (policy) እንድንተዳደር የተፈለገው? በጣም የሚገርም እኮነው! እንደ አቶ ኢሳይያስ ያለ የድንጋይ ዳቦ ዘመን ብልጥ ሰው አጋጥሟቹህ ያውቃል? ለመሆኑ እንዲህ ዓይነት ግንኙነት ተጎዳኝተን ስናበቃ ሀገራችንን ማን እንድንላት ነበር ያሰቡት አቶ ኢሳይያስ? የተባበረችው ኢትዮጵያ ነው ወይስ ሌላ ስም ነበረዎት? ለካ የአፍሪካ ሲንጋፖርን የመፍጠር ሕልምዎን እውን ሊያደርጉት ያሰቡት በሀገራችን ሀብት ኖሯል? ባይሆንማ ኖሮ እነሆ ሲንጋፖር ሲሆኑ እናይዎት አልነበር! ለነገሩ እርስዎ ምን ያድርጉ ይሄንን እንዲያስቡ ያስገደደዎት ባሕረ ምድርን ከገነጠሉ በኋላ ባሕረ ምድርን እንደሀገር ህልውናዋን ለማስቀጠል ብሎም ለእድገት ብልጽግና ለማብቃት የሚያበቃ የተፈጥሮ ሀብት አልባ ሀገር ሆነችብዎት አይደል? ማጣፊያው አጠረብዎት አይደል? ሲጨንቅዎት ምን ያድርጉ? ያለዎት አማራጭ ሀገራችንን እየቦጠቦጡ የአፍሪካን ሲንጋፖር ማለም ነው፡፡

“የምን ዐይነ ደረቅ” የሚባለው ነገር ነው የሆነብን፡፡ አዩት አይደል የእርስዎን (የሕዝባዊ ግንባርን) ስሕተት? ሀገር እንደ ገበሬ ጓሮ ለብቻየ ተብሎ የሚፈጠር ነገር አለመሆኑን ተረዱት አይደል? ሀገር ሲታሰብ ብዙ ነገር ያስፈልጋል፡፡ ይሄንን ሁሉ ነገር ቀድሞ ለማየት ለመገመት የሚችል ጭንቅላት ስላልነበረዎት ይህ የገጠመዎት ችግር በፊት አልታየዎትም ነበር፡፡ በእርስዎ እውቀትና እምነት አንድ የሆነ መሬትን ቆርሶ ወይም ገንጥሎ መውሰድ ከተቻለ ሀገር የሚሆን ይመስልዎት ነበር፡፡ የሚያሳዝነኝ ነገር እንዲህ እንደእርስዎ ባሉ ሰዎች የሕዝብ ዕጣ ፋንታ መወሰኑ ብቻ ሳይሆን ድርጊታቹህ የተሳሳተ እንደነበር ብታውቁም ተሳሳቱ ላለመባል ብቻ አምናቹህ አለመቀበላቹህና ለመታረም ባለመፈለግ ሕዝብን ተጨማሪ ዋጋ እንዲከፍል ማድረጋቹህ ነው፡፡ ስሕተትን ለመሸፈን መፍትሔ አድርጋቹህ ለመውሰድ የምትፈልጉት ጉዳይ ደግሞ ነገሩን ይባስ ከድጡ ወደ ማጡ የሚወስድ መሆኑ ነው ሌላው የሚገርመው ነገር፡፡ አሁንም ይህን መፍትሔ አድርጋቹህ ያያቹህትን ነገር ለዘለቄታው ማርድረግ ይቻላል ወይ? ብላቹህ ለማሰብ አለመቻላቹህ አሁንም ደካማ የማሰብ ችሎታቹህን የሚያሳይ ነው፡፡ አቶ ኢሳይያስ ፈጽሞ የፖለቲከኛ ጭንቅላት የለዎትም ሌላ ሊሠሩ የሚችሉት ነገር ካለ ትተውት ቢሄዱ መልካም ነው፡፡ እንዴ! እርስዎና ወያኔ የምትገርሙኝ ነገር ቢኖር እናንተ ያልቻላቹህበት እንደሆነ በእናንተ ስሕተቶች እኛ መሰቃየት አለብን እንዴ? ምናለ ሐፍረት ቢሰማቹህ? ምን ዓይነት ሰብእና ቢኖራቹህ ነው ሐፍረት የሚባል ነገር ጨርሶ ሊሰማቹህ የማይችለው? ለማንኛውም ሲያምርዎት ይቅር እርስዎና ቢጤዎችዎ ከድንቁርና ቅዠታቹህ ጋር ገሀነም ትወርዳላቹህ እንጅ ኢትዮጵያን በመቦጥቦጥ ሲንጋፖርን መሆን አይቻልም፡፡

ሌላው ደግሞ አቶ ኢሳይያስ ምን አሉ? “እኔ ስለ 3ሽህ ወይም ከዚያ በላይ ዓመታት ስላለው ታሪክ ማውራት አልፈልግም ማውራት የምፈልገው ከ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ወዲህ ያለውን ነው፡፡ ብዙ ጊዜ 20ኛው መቶ ክ/ዘ ታሪክ የአፍሪካ ሀገሮች ታሪክ ብለን ስንል የ 19ኛው መቶ ክ/ዘ መጨረሻ ታሪክ ማለታችን ነው፡፡ ምክንያቱም የቅኝ ግዛት ድንበር የሚባለው ነገር የሚመጣው ያኔ ነው፡፡ ከዚያ ውጭ ግን የአጋንንት ሳጥን (Pandora’s box) ምናልባት 19ኛው ወይም 18ኛው መቶ ክ/ዘ ቅኝ ግዛት ከመምጣቱ በፊት ይሄ አካባቢ ምን ይመስል ነበር? ብሎ መነጋገር ይቻል ይሆናል ይሄ ግን ሌላ ርእስ ነው እኛ አሁን ያለንበት ከአፍሪካ በቅኝ ግዛት መከፋፈል በኋላ የተፈጠረ ስለሆነ የኛ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው” በማለት ስለ እሳቸው እኔ ያፈርኩላቸውን ነገር ተናገሩ፡፡ አቶ ኢሳይያስ በእርስዎ ቤት መሳደብዎ ነው አይደል?

አቶ ኢሳይያስ ይሄንን የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን አዋጅ እየደጋገሙ የሚያነሡበት ምክንያት ቅኝ ገዣቸው ባሕረ ምርድ የሚለውን ኢትዮጵያን ሰሜናዊ ክፍል በኃይል ቆርጠው ስም ቀይረው ኤርትራ በማለት አዲስ ባወጡላት ስም የሚጠሯት ሀገራቸው ህልውና ከመቸ እንደሚጀምርና በአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአፍሪካ ኅብረት) አዋጅ መሠረትም የሀገር ህልውና እንደሚኖራት ለመሟገት ነው፡፡ ወደዚህ ዝርዝር ከመግባቴ በፊት ግን አቶ ኢሳይያስ የግሪኮችን ተረት (myth) አውቃለሁ ለማለት የአጋንንት ሳጥን (Pandora’s Box) “ላስተካክልላቸውና የፓንዶራ የአጋንንት ሳጥን ነው የሚባለው” ስለሱ ጥቂት ልበል፡፡ ይገርማል አቶ ኢሳይያስ ቅድመ 19ኛው መቶ ክ/ዘ ያለውን ታሪካችንን በፓንዶራ የአጋንንት ሳጥን (Pandora’s Box) መስለውታል፡፡ ይሄ ሰውየው ለሀገራችን ታሪክ ያላቸውን ከባድና ጤነኛ ያልሆነ ጥላቻ ያሳያል፡፡ ለመሆኑ የአጋንንት ሳጥን መባል ካለበት መባል ያለበት የትኛው ዘመን ነው አቶ ኢሳይያስ? እንዲያው ምን ዓይነት ጭንቅላት ቢኖርዎ እንዴትስ ቢያስቡ ነው ከነጻነቱ የአገርዎ ባለቤት ከነበሩበት ሕዝቡ በነጻነት የሀገሩ ባለቤት ሆኖ ይኖር የነበረበት ዘመን የአጋንንት ሳጥን ሆኖ በቅኝ ገዥ ተጠፍንጎ በገዛ ሀገሩ ባዕድ ሆኖ እንደ መገልገያ ዕቃ ተቆጥሮ በባርነት በግዞት በጭቆና የኖረበት ደግኖ የመላእክት ሳጥን የሚሆንበት በምን ሒሳብ በምን መመዘኛ ነው አቶ ኢሳይያስ? ግን ጤነኛ ነዎት ለመሆኑ?

አቶ ኢሳይያስን ልጠይቅ የምሻው ነገር ፍጹም እንከን ወይም የእርስ በእርስ ግጭት የሌለበት በተለይ ደግሞ እኛን በመሰለ የረጅም ዘመን ታሪክ ባላቸው ሀገራት ምንም ኮሽታ ያልነበረበት ሀገር አንድ እንኳን ሊጠቅሱልኝ ይችላሉ? ከእነዚህ ሀገራት ውስጥም በአንፃራዊ መልኩ ሲታይ ከእኛ የተሻለ ሰብአዊነት የነበረበት ሀገር አንድ እንኳን ሊጠቅሱልኝ ይችላሉ? ይሄንን ለማለት የሚያስችልዎት እርስዎ ባሉበት አካባቢና በተቀረው የኢትዮጵያ ክፍል መካከል የተፈጠረ ይሄንን ያህል አማረው ሊያወሩት የሚችሉት ነገር ምንድን ነው? ተብለው ቢጠየቁ ምን ብለው ሊመልሱ ነው በፓንዶራ የአጋንንት ሳጥን እስከመመሰል ያደረሰዎት? ትንሽ እንኳን ይታዘቡኛል ምን ይሉኛል አይሉም? እስኪ በሞቴ ይሄ ይሄ ይሄ ብለው ቆጥረው ይንገሩን? አሁን ምንም ማለት አልፈልግም ይሄ ይሄ ብለው የተናገሩ ዕለት ግን በሚገባ የምልዎት ነገር ይኖራል፡፡ ምንም ነገር ሳይናገሩ በደፈናው አጨፍግገው አከፋፍተው በመናገር በዜጎችዎ ጭንቅላት ውስጥ ስለ ኢትዮጵያና ሕዝቧ መጥፎ ሥዕል በመሳል ያንን ዘመን እንዲጠሉ ለማድረግ የሚያደርጉትን ጥረት ግን ቢተውት ይሻላል፡፡ አለዛ ግን ከፆታ ልዩነት በስተቀር ፓንዶራን እራሷን ሆነው እየተወኑ እንደሆን ልብ ሊሉት ይገባል፡፡

በጣም የሚገርመው አቶ ኢሳይያስን የሚያኮራቸው ሲያወሩትም ደስ የሚላቸው ዋጋ የሚሰጡትና የሚወዱት ከ19ኛው መቶ ክ/ዘ በፊት የነበረውን የነጻነቱን የአንድነቱንና ብርቅየውን የፍቅሩን አኩሪውን የሚያስቀናውን ታሪክ ሳይሆን ከ19ኛው መቶ ከ/ዘ ወዲህ ያለው የባርነቱን፣ እንደ ሰው ሳይሆን እንደ እንስሳ ተቆጥረው የተገጠቡበትን፣ ሰብአዊ ክብራቸው ተገፎ እንደ ዕቃ የተቆጠሩበትን፣ የሰቆቃውን የውርደቱን ዘመን መሆኑ ሰውየው ያለበትን የሞራል (የቅስም) ደረጃ ዝቅጠት ውድቀትና ኪሳራ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ እጅግ ይገርማል የሚያሳፍረው ያኮራዋል ሲያወራውም ያስደስተዋል የሚያኮራው ግን ያሳፍረዋል ጨርሶም ሊያወራው አይፈልግም፡፡ አይገርምም? “ለምን ምን አይጥማትም” ነበር ያለው ያገሬ ሰው? ይህ አስተሳሰብ የአጠቃላይ የሕዝቡ እንዳልሆነ ተስፋ ላድርግ ይሆን? እኔ የምልዎ አቶ ኢሳይያስ እርስዎና መሰሎችዎ እንዲያው ከቅኝ ግዛት ምን ብትጠቀሙ ነው ለቅኝ ግዛት ያላቹህ ፍቅር ይሄንን ያህል የቅኝ ግዛትን ውርስ ለማስጠበቅ መሥዋዕትነት እስከመክፈል ድረስ ያደረሳቹህ? ባንዳነት እኮ ያሳፍራል! አያሳፍርም እንዴ አቶ ኢሳይያስ? ለእናንተ እንጃ ለኛ ለነጻነት ታላቅ ቦታና ዋጋ ለምንሰጠው ለሱም ምንም የምስሰስተው ነገር ለሌለን ኢትዮጵያዊያን ግን እጅግ አሳፋሪ አስነዋሪ አዋራጅ ርካሽ ወራዳ ማንነት ነው፡፡

አቶ ኢሳይያስ ቅኝ ገዢዎች ኢትዮጵያን ከሦስት ሊከፍሏት ፈልገው የነበሩት ለምን ይመስልዎታል? የባርነትዎን ውርስ እንደታላቅ ቅርስ እስከ መጨረሻው ለመጠበቅ ቁርጠኛ በመሆንዎ ሕዝብዎ ካላፈረብዎት በሌላ በምንም የሚያፍር አይሆንም፡፡ ከሽዎች ዓመታቱ የአንድነት የከበረ ታሪካችን ይልቅ ለ60 ዓመታቱ የባርነት የጭቆና ታሪክ ይንሰፈሰፉለታል ይንገበገቡለታል ያስቡለታል ይሄ በፍጹም የጤና አይደለም፡፡ ጤነኛ ሰው እንዴት ከወንድሙ ይልቅ በመረረ ግፍና ጭቆና እንደ አሕያ ሲገጥበው የኖረውን ጠላት ይወዳል? ምን እያልኩዎት እንደሆነ ይገባዎታል አቶ ኢሳይያስ? የባርነትን ውርስ በመጠበቅ በመንከባከብ እያስፈጸሙ ያሉት የነዚያን ግፈኞች አረመኔዎች የቅኝ ገዥዎችን ዕቅድና ዓላማ ነው ይሄ ደግሞ ባንዳነት ነው ባርነት ነው ነጻ ወጥቻለሁ ነጻ ነኝ ብለው እንዳያስቡ፡፡ ጭንቅላት ቢኖርዎት ማሰብ ቢችሉ በዚህ እጅግ ሊያፍሩ ሊሸማቀቁ እንጂ እያየንዎት እንዳለው ሊኮሩ ሊኮፈሱ አይገባም ነው እያልኩዎት ያለሁት፡፡ ይሄ ይገባዎት ይሆን አቶ ኢሳይያስ? ሕዝብዎንስ ይገባው ይሆን? እርግጠኛ ባልሆንም ታፍነው ተይዘው እንጅ የሚገባቸው ይኖራሉ ብየ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ግፈኞቹ ቅኝ ገዥዎች ባሕረ ምድርን ከኢትዮጵያ ቆርጠው ይዘው ነበር ዛሬ እነሱ የሉም፡፡ እነሱ በሌሉበት ሁኔታ የግፈኞችን ሕልምና ዓላማ ውርስ በማስቀጠል ባሕረ ምድርን ከኢትዮጵያ እንደተቆረጠች ለማስቀረት መጣር የፋሽስት ዝግንትል ተሸካሚነት (አህያነት) አይደለም ወይ? የሄስ አያሳፍርም ወይ? ያውም እኮ የሚያዋጣ በሆነ ምንም ባልነበር ነገር ግን ጨርሶ የማያዋጣ በሆነበት ሁሌታ እንዲህ መሆን ከአህያም አህያነት አይደለም ወይ? እኔ ምንም አልገባ አለኝ እንዴት ነው የምታስቡት?

እናንተ ብዙ ጊዜ የምታነሡት ነገር አለ “ዐፄ ምንሊክ ሸጠውናል ተከድተናል” የሚል ስለ እውነት ለመናገር ታሪክ ያነበበ በወቅቱ የሆነውን በሚገባ የተረዳ ሰው የሚያስብና የሚያገናዝብ ጭንቅላት ያለው ሰው በእርግጠኝነት ይሄንን አይልም፡፡ የእናንተ ችግር ሲጀመር ታሪኩን የነበረውን ሁኔታ በንጹሕ ሕሊና ለማየት አለመሞከራቹህ አለመፈለጋቹህ ነው፡፡ ይሄንን ለማለት የሚያስደፍረኝ ነገር ከአድዋ ጦርነት ዋዜማ በኢትዮጵያ ምን ተከስቶ እንደነበር ያውቃሉ? “ክፉ ቀን” በመባል የሚታወቀው በሀገሪቱ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የድርቅ ሳይሆን የረሀብ ወቅት ነበር፡፡ ድርቅ ሳይኖር እንዴት ያውም ከባድ ረሀብ ሊኖር ቻለ ይሉ ይሆናል፡፡ የዚህ ምክንያቱ ረሀቡ የተፈጠረው በሰው ሰራሽ ችግር እንጅ በተፈጥሮ አለመሆኑ ነው፡፡ ረሀቡ የተፈጠረው ጣሊያን ከጦርነቱ ከዓመታት በፊት ሀገሪቱንና ሕዝቧን ለቅኝ ግዛት እጅ እንዲሰጡ ለማድረግ የከብት በሽታ ከህንድ አስገብቶ ከብቶችን በመውጋት ከብቱ ሁሉ እንዲያል ስላደረገ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ነው እጅግ አስከፊው “ክፉ ቀን” የሚባለው ረሀብ ሊከሰት የቻለው፡፡ የግብርናው አከርካሪ በመሰበሩ ምክንያት፡፡ “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንዲሉ ሕዝባችን በዚህ መከራ ላይ እያለ ነበር የአድዋ ጦርነት የመጣው ሀበሻ ከነጻነቱ የሚያደርሰውና ለነጻነቱ የማይከፍለው የመሥዋዕትነት ዓይነት ባለመኖሩ በረሀብ የደከመ የኮሰመነ ጉልበቱን ይዞ ነገር ግን እንደ አሳተጎመራ የሚፋጅ የሚገነፍል ወኔውንና የሀገር ፍቅሩን ይዞ ነበር ወደ አድዋ የዘመተው፡፡ ከድሉ በሏላ ገፍቶ በመሔድ ባሕረ ምድርንም ማስለቀቅ ጠፍቶት አልነበረም በመቶ ዐሥር ሽህ ከሚቆጠረው ዘማች (በእርግጥ ጣሊያኖች ቁጥሩን እስከ 160 ሽህ ድረስ ያደርሱታል በቁጥር ብልጫ ስለተወሰደብን ነው የተሸነፍነው ለማለት ነው እንጅ ሐሰት ነው) ከዚህ ሠራዊት ከፊሉ ለአርበኞች ምግብ የሚያበስሉ ሲቆስሉ የሚንከባከቡና የተለያየ አገልግሎት የሚሰጡ ሴቶችና የሚቆዩበት ባለመኖሩ ከወላጆቻቸው ጋር የሔዱ ሕፃናት ናቸው፣ ከሃያ ሽህ በላይ የሚሆነው በጦርነቱ የተሠዋና ቁስለኛ ነበር፣ ሠራዊቱ ስንቅ ጨርሷል ለመሰንበቻ ያህል ከአካባቢው ሰው ለመሸመት ቢፈለግም አንዲት እፍኝ እንኳን ሊገኝ አልቻለም፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይ የነበረ ሠራዊት እንዴት ብሎ ነው ገፍቶ በመሔድ ምናልባትም ከአድዋ የከበደ ጦርነትን ሊያደርግ የሚችለው? ነው ወይስ ተሸንፎ መላዋ ኢትዮጵያ በባርነት ሥር መውደቅ ነበረባት ማለታቹህ ነው?

በዚህ ላይ ደግሞ በጣም የሚገርመውና ሳልነግርዎት ማለፍ የማልፈልገው ነገር ከጣሊያን ወራሪ ሠራዊት ውስጥ ከዓረቦችና ከጣሊያኖች በላቀ ቁጥር በባንዳነት ከጣሊያን ጋር ተሰልፎ የገዛ ሀገሩንና ወገኑን ይወጋ የነበረው የእርስዎ ወገኖች እንደነበሩ ያውቁ ይሆን? ይሄንንም ግንዛቤ ውስጥ ብታስገቡ መልካም ነው፡፡ እናንተ የምታግዙ ቢሆን ነገሩ ምንኛ ቀላል በነበረ ነበር የሆነው ግን ሌላ ነው እናንተም እራሳቹህ ከጣሊያን ጋር ተሰልፋቹህ ሀገር ወገናቹህን የምትወጉበት ሁኔታ ነው የነበረው፡፡ ይሄ ይሄ ሁሉ እያለ አይከብድም አቶ ኢሳይያስ? ስለዚህ ያለው አማራጭ መመለስና ጣሊያንን በውልና በአንዳንድ ነገሮች እዛው ባለበት አስሮ ለማቆየት ጥረት በማድረግ ዕረፍት ወስዶና ጊዜ ወስዶ ተጠናክሮ መመለሱ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ስለሆነባቸው ነው የተመለሱት፡፡

አቶ ኢሳይያስ እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቅዎት አምላክ ታደገን እንጅ ፋሽስት ጣሊያንን የ1928ቱ ወረራው ወደ ቅኝ ግዛት አሸጋግሮት መላዋን ኢትዮጵያን ቅኝ መግዛት ችሎ ቢሆንና ሀገራችን እንደሌሎቹ ሀገራት ከጊዜ በኋላ ነጻ ወጥታ ቢሆን ኖሮ ይሄንን የጠቀሱትን የአፍሪክ አንድነት ድርጅት አዋጅ ያነሡ ወይም ማንሣት ይችሉ ነበር? አዩ አይደል ለዚህ ነው የባርነትን ውርስ ለመጠበቅ ለመንከባከብ ህያው ለማድረግ የሚሠሩ ባሪያ ነዎት የምልዎት፡፡ እያልኩዎት ያለሁት ነገር ይገባዎታል? እያልኩ ያለሁት እርስዎ የሚሉትን ነገር ሁሉ ፋሽስት ጣሊያን ከ40 ዓመታት በኋላ በ1928 ባደረገው ወረራ እንዳይሠራ አድርጎታል ነው እያልኩዎት ያለሁት፡፡ ሰው እንዴት ከባርነት ጋር ፍቅር ይወድቃል? ኧረ እባካቹህ ንቁ በእናንተ ይብቃ ልጆቻቹህንም የባርነት አስተሳሰብ ሰለባ አታድርጓቸው ነጻ ይውጡ ሰዎች እንጅ ጣሊያን ሲገጥባቸው እንደነበሩት አያቶቻቸው ባሪያዎችና የቅኝ ገዥ አጋሰሶች አታድርጓቸው፡፡

በተለይ ደግሞ ሊያስቡ የሚገባው ነገር በሌሎች የአፍሪካ ሀገራትና በቅኝ ገዥዎቻቸው መሀከል የነበረው ሁኔታና ግንኙነት በኢትዮጵያና በጣሊያን መሀከል ከነበረው ሁኔታና ግንኙነት ፍጹም የተለያየና ምንም የሚያገናኘው ነገር ስለሌለ “የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አዋጅ” እያሉ የሚጠቅሱት ድንጋጌ እኛን አይገዛንም በእኛ ላይ አይሠራም፡፡ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ለአንድ ሀገር ብሎ የተለየ አዋጅ ማውጣት ስለሌለበት ሁኔታው በግልጽ ስለሚታወቅ ማንም ሊገነዘበው ስለሚችል ነው የተለየ ሕግ ለኢትዮጵያ ያላወጡት፡፡ በእኛና በጣሊያን መሀከል የነበረው ነባራዊ ሁኔታ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች የተለየ በመሆኑ፡፡ ስለሆነም ይሄንን አዋጅ እንደመተማመኛ ሰነድ አድርገው መቁጠርዎን ያቆማሉ፡፡ እስኪ ሌላ ጥያቄ ልጠይቅዎት ይህ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አዋጅ በሶማሊያ ላይ ለምን ያልሠራ ይመስልዎታል? እንደ እርስዎ እምነት ቢሆን ኖሮ እኮ ሶማሊያ ሁለት ሀገር መሆን ነበረባት፡፡ የእንግሊዝ ሶማሌ (ሶማሌ ላንድ) እና የጣሊያን ሶማሌ ተብለው የተለያዩ ሀገራት መሆን ነበረባቸው፡፡ ነገር ግን ያ አልሆነም፡፡ አሁን ሶማሊያ ከፈራረሰች በኋላ ሶማሌ ላንድ “እኔ ሰላም ነኝ እራሴን ችየ ተነጥያለሁ እራሴንም እያሥተዳደርኩ ነኝ እባካቹህ ዕውቅና ይገባኛል እውቅና ስጡኝ?” እያለች ስትጮህ የአፍሪካ ኅብረትን ጨምሮ ምዕራባዊያን የተቀረውም የዓለም ክፍል ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ዕውቅናውን የነፈጋት ለምን ይመስልዎታል? ስለሆነም ዐሥሬ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አዋጅ እያሉ አያላዝኑብን እንኳንና በኛ በነጻዋ ሀገር በሱማሌም አልሠራም፡፡ ለዚህም ነው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባሕረ ምድርን ወደ እናት ሀገሯ እንድትቀላቀል የወሰነው፡፡

እኛ እኮ እንዲያው የአባቶቻችንን አዳራ ለመጠበቅ የሀገራችንን የግዛት አንድነት ላለማስደፈር ያስረከቡንን እንደተረከብን አድርገን ለተከታይ ትውልድ ለማስረከብ  በሚል ነው እንጅ እኮ እንዲህ የምንንገበገበው አንዳች ጥቅም ኖሯቹህ እኮ አይደለም፡፡ እንኳን ለኛ እራሳቹህ ለራሳቹህ እንኳን እንዳልጠቀማቹህ እያያቹህት ነው፡፡ እናም አደራ ለመጠበቅ ስንል ብቻ በሕገ ወጥ መንገድ ከእናት ሀገሯ የተቆረጠችውን ባሕረ ምድርን ወደ እናት ሀገሯ እንመልሳታለን፡፡ በክህደት የተመረዛቹህና ኢትዮጵያዊያን አይደለንም ኢትዮጵያዊ መሆን አንፈልግም የምትሉ ካላቹህ ተጠራርጋቹህ ቀይ ባሕር ልትገቡ ትችላላቹህ፡፡ መሬታችንን ግን እናት አባቶቻችን ደምና አጥንታቸውን ያፈሰሱ የከሰከሱበትን ምድር ግን እንመልሳለን፡፡ ካዘንንላቹህ ደግሞ አላግባብ በወያኔ የክህደት ሥራ በልግስና የተሰጣቹህን አሰብን ወደ ሀገሩ መልሰን “መንገዱን ጨርቅ ያርግላቹህ” ብለን መርቀን እንሸኛቹሀለን የት እንደምትደርሱ እናያለን፡፡ ከዚያ በኋላ ግን “ኧረ ኢትዮጵያዊያን ነን መልሱን እሪ ያገር ያለህ” ብትሉም እንኳ አንፈልግም ይህ የናንተ ትውልድ ለመገንጠል ብረት እንዳነሣ ሁሉ ቀጣዩ ትውልዳቹህ ደግሞ ለመዋሐድ ብረት የሚያነሣ ይሆናል፡፡

እንግዲህ አቶ ኢሳይያስ በቃለመጠይቃቸው የቀበጣጠሩት የባጥ የቆጡንና የተንዛዛም ስለነበር ተንዛዝተው ሲያበቁ እኔንም አንዛዙኝ፡፡ በሌላው ጉዳይም ሁሉ መልስ ልስጥ ብል እሳቸውን መሆን ስለሚሆን በዚሁ ይብቃኝ፡፡ ከመቋጨቴ በፊት ግን በትጥቅ ትግል እዚያ ላሉ ወገኖቻችን የማስተላልፈው መልዕክት አለኝ፡- ወገኖቸ ሸአቢያ ሸአቢያ ነው፡፡ መቸም ቢሆን ከሸአቢያነቱ ሊለወጥ አይችልም፡፡ ሸአቢያን ከሸአቢያነቱ ወያኔንንም ከወያኔነቱ መለወጥ ማለት ሰይጣንን ወደ መልአክነት መለወጥ መቻል ማለት ነው ፈጽሞ የማይቻል የማይሆን ነገር ነው፡፡ ስለሆነም በምንም ተአምር ቢሆን በሸአቢያ ላይ እምነት እንዳትጥሉ፡፡ አማራጭ የለምና የትጥቅ ትግሉን እዚያው ማድረግ ግድ ነው፡፡ ሸአቢያ ይሄንን ዕድል በመስጠቱ ውለታ እንደሠራልን እንዳትቆጥሩት፡፡ እሱ ሊያደርገው የማይችለውንና መቸም የማያገኘውን ዕድል ነው በእናንተ ምክንያት ያገኘው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ልብና ድጋፍ ከእናንተ ጋር ነው ይሄ ማለት በወያኔና በሸአቢያ መሀከል ጦርነት ቢነሣ እንደ ባለፈው ሁሉ ሕዝቡ ሆ ብሎ ከወያኔ ጋራ ተሰልፎ ሸአቢያን አይወጋም እንኳንና ሕዝቡ ወታደሩም እንኳን ቢሆን ይሄንን አያደርግም ይሄንን የሚያደርገው ለሸአቢያ በማዘን ሳይሆን ለእሱ ስትሉ በረሀ ስለገባቹህት ስለእናንተ ሲል ነው፡፡ ሸአቢያ ለእናንተ ቦታ በመስጠቱ ወይም በመርዳቱ ምክንያት ይሄንን ታላቅ ጥቅምና አጋጣሚ ማግኘት ችሏል በዚህም ምክንያት ከወያኔ ጋራ ጦርነት ቢገጥም በቀላሉ ሊያሸንፍ የሚችልበትን ዕድል አግኝቷል፡፡ ይሄ ነው የውለታው ክፍያ፡፡ ያደረገው ለራሱ ጥቅም ሲል እንጅ ለኛ ወይም ለኢትዮጵያ አይደለም፡፡ መችም መቸም ሊያገኘው የማይችለውን ጠላቱን እንዲበቀል የማድረግ ዕድሉን እንዲያገኝ አድርገናልና ውለታው በዚህ ተመልሷል፡፡ ሌላ ክፍያ ሊጠብቅ አይደለም ሊያስብ እንኳን አይገባም፡፡ ነገር ግን ሸአቢያ ልብና ማስተዋል ጭንቅላት የለውምና እንዲህ ስላደረኩላቹህ ወይም ስለማደርግላቹህ እንዲህ ታደርጉልኛላቹህ እያለ አስጨንቆ ቢይዛቹህ አሽ በሉት ፈርሙም ካላቹህ በዐሥር ጣቶቻቹህ ፈርሙለት ይሄንን ባለማድረጋቹህ እናንተን ማጣት አንፈልግምና፡፡ ልባቹህን እናውቀዋለንና ተገዳቹህ የውሸት የፈረማቹህለትን ፊርማ በመፈረማቹህ ክህደት እንደፈጸማቹህ አንቆጥርም፡፡ ታደርጉልኛላቹህ ያላቹህ ነገር ሊከፈለው የሚችለው እዚህ ሀገራቹህ ገብታቹህ በምድራቹህ ሆናቹህ ወያኔን አስወግዳቹህ ነውና ሊሆን የሚችለው ከሕገ ወጥና ከከሀዲ ጋር የተደረገ ውል አይጸናምና ያኔ አፍንጫህን ላስ ብንለው በሀገራቹህ በምድራቹህ ከወገናቹህ ጋር ሆናቹህ ነውና ምንም ሊያመጣ አይችልም፡፡ በጅብ ሀገር እንደ ጅብ መጮህ ግድ ይላል፡፡ መድኃኔዓለም ከናንተ ጋር ይሁን!!!

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

 

The post አስቂኙ የአቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ቃለ መጠይቅ! – ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው appeared first on Zehabesha Amharic.


መኢአድ በወያኔ ሚዲያዎች በኢቢሲ በፋና በዛሚ እንዳያቀርበዉ የተከለከለዉ ጽሑፍ

$
0
0

የተወደድክና የተከበርከው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!

aeupከዘመናት በፊት የሥልጣኔ ችቦ ከተቀጣጠለባቸው ጥቂት አገሮች መካከል አገራችን ኢትዮጵያ አንዷ ናት፡፡ በዚህ ረጅም የሥልጣኔና
የታሪክ ዘመን ውስጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ በተለያዩ መንገዶችና በማንኛውም ሁኔታ ነፃነቱን ለማስከበር ከውጭ ወራሪ ሐይሎች
ጋር ሲታገል መኖሩ የዓለምን ሕዝብ ቀልብ ከመሳቡ ባሻገር ለአፍሪካውያንና በዓለም ላይ ላሉ ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት አርአያና
ተመሳሌት በመሆን የጥቁርን ዘር ክንድ ብርታትና ፅኑነቱን አስመስክሯል፡፡ ይህ አስደናቂና ወደር የማይገኝለት ድል ዘወትር
የሚከነክናቸው ባእዳን የሀገር ውስጥ ባንዳዎችን በማዘጋጀትና ግንባር ቀደም ተዋናይ በመሆን ብዙና ከባድ የችግር ቀንበር
ሊጭኑበት ሞክረዋል በዚህ ምክንያት ህዝባችን ዘርፈ ብዙ መስዋዕትነትን እንዳከፍልም ሆኗል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነቱን፣ ታሪኩን፣ ሉዓላዊነቱንና ባህሉን ለሦስት ሺህ ዓመታት ጠብቆ የኖረ መሆኑን ዓለም ይመሰክራል፡፡
ሕዝባችን በውስጥ አስተዳድር የደላውና የተመቸው ባይሆንም ቅሉ ብሶቱን አቻችሎ የአገሩን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት ለማስከበር
ዘር፣ ጐሳ፣ ቀለምና መንደር ሳይለየው በደሙ እየዋጀ መተኪያ የሌላት ሕይወቱንም ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
የኢህአዴግ መንግሥት ሥልጣን ከያዘበት ቀን ጀምሮ ይህን በደምና በአጥንት የተገነባ ዳር ድንበር እንዲጣስ በማድረግ
ለባእድ ፈቅዶ በመሥጠት ወደብ አልባ አድርጐናል፡፡ ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ጥቅም እንዲሁም የሕዝቧን ግለሰባዊና ቡድናዊ
ነጻነትና ደህንነት በተገቢው መንገድ ማስጠበቅ ስላልቻለ ድርጊቱን በመቃወም ለመታገል የመላው ኢትዮጵያ አንድነት
ድርጅት /መኢአድ/ በሕብረ ብሔራዊና አገር አቀፍ ፓርቲነት በቁርጥ ቀን ልጆች ተመሰረተ፡፡
ኢህአዴግ የደርግን መንግሥት ተክቶ ሥልጣን ከያዘበት ቀን ጀምሮ ይመጣል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረውን የአገር አንድነት፣
ሰብአዊ መብት መከበር፣ የዲሞክራሲ መጎልበት ሒደት ቀልብሶ የኢትዮጵያን ሕዝብ ዘርና ቋንቋን መስፈርት ባደረገ የክፍፍል
ቀለበት ውስጥ አስገብቶ እርስ በእርሱ እንዲናቆር የሚአደረግ ሥልት ዘረጋ፡፡ ሕዝባችንም በተወለደባት አገር ከቦታ ቦታ
በመዘዋወር በነጻነት መሥራት እንዳይችል በተደረገበት ወቅት መኢአድ ይህን ለአገርና ለትውልድ የማይበጅ ድርጊት በመቃወም
የኢትዮጵያን ሕዝብ አስተባብሮ ሉአላዊነቷ የተጠበቀ፣ እድገቷ የተፋጠነና የህግ የበላይነት የሰፈነባት ዲሞከራሲያዊት ኢትዮጵያን
ለመገንባት የተቋቋመ አንጋፋ ድርጅት ነው፡፡ መኢአድ የህን ለአገርና ለትውልድ የማይበጅ ሥርዓት ሲታገል
ቆይቷል፤ በመታገል ላይም ይገኛል፡፡ መኢአድ ይህን እንቅስቃሴ ሲያደርግ በነበረበት ወቅትም ትግሉ አልጋ በአልጋ አልነበረምና
የገዥው ፓርቲ ካድሬዎችና አመራሮች በፓርቲው መሪዎች፣ አባላቶችና ደጋፊዎች ላይ ከፍተኛ የሆነና ግፍ የተሞላበት
ድብደባ፣ መሳደድና፣ የመታሰርና የመገደል ዕጣ ሲደርሱባቸው ቆይተዋል፡፡
እጅግ ዘርፈ ብዙ ችግሮች የሚቀየር ቢሆንም የሕዝብ ጥያቄ የሆነውን የነፃነት፣ የሕግ የበላይነት መስፈን፣ የሰብዓዊና
ዲሞክራሲያዊ መብቶች መከበር ለሚደረገው ትግል የኢትዮጵያን ሕዝብ ለመምራት በግንባር ቀደምትነት ብቸኛውና ጥንካሬውን
ያስመሰከረው የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ተስፋ የሆነው መኢአድ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ያደረገው ሕዝባዊ
ትግል የኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን የዓለምን ሕብረተሰብ ትኩረት በመሳብ ላይ ይገኛል፡፡ መኢአድ ከስሙ መረዳት
እንደሚቻለው ሕዝባችን በአንድነት በእኩልነትና በመፈቃቀር እንደኖር አስተማማኝ ፖሊሲዎችን ነድፎ ተግባራዊ ለማድረግ
በመላ አገሪቱ በመንቀሳቀስ ላይ ያለ ሀቀኛ የፖለቲካ ድርጅት ነው፡፡
መኢአድ ይህንን ታሪካዊና ህዝባዊ ሃላፊነት ለመወጣት ሲል በሚያደርገው ሁሉንተናዊ የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ የገዥው
ፓርቲ ኢህአዴግ ከቅድመ ምርጫ 97 ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ በፓርቲው አባላት ላይ ከፍተኛ እንቅፋት መፍጠሩ የቀን ከቀን
ትዕይንት ሆኖ ቀጥሎአል፡፡ ኢህአዴግ ይህን ሁሉ ቢፈጽምም ሚስማር ሲመታ ይጠብቃል እንደሚባለው ሁሉ መኢአድ በአባላቱ
ላይ የሚደርስበትን ዘርፈ ብዙ ተፅዕኖ፣ ችግርና ሰቆቃ በመቋቋም ለሕዝብና ለሀገር የሚጠቅም ሥራ በመስራት የኢትዮጰያን ትንሳኤ
ለማየት ህዝባዊና ሀገራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ላይ ይገኛል፡፡ አሁን በሀገራችን ኢትዮጵያ የሚታዩት ከዚህ ቀደም ያለፉት የገዥ
መደቦች የሕዝብ ምርጫና ሰላማዊ መንገድ የሥልጣን ሽግግር ባለመከናወናቸው ኢህአደግም ያንን በመከተል ከማንወጣው
ችግር ውስጥ እንድንገባ ተደርገናል ያለፉት የገዢው መደቦች ሰላማዊ ነፃና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዳይኖር ሕዝቡን በአንድ
ወጥ የአገዛዝ ቀንበር ከሥረው ያቆዩትን ጨቋኝ ልማድ ኢህአዴግ በመረከብ ከህዝባዊ ምርጫ ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር
እንዳይኖር በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
የኢትዮጵያ ሕዝብ ከብዙ ሺህ አመታት የነፃነት ታሪካችን ባለተናነሰ ሁኔታ በዘር በቋንቋና በጉሳ ሳይለያይ በፍፁም ወንድማማችነት፣
መከባበር፣ መፈቃቀርና መቻቻል አብሮ መኖሩን ታሪክ ይመሰክራል፡፡ ዛሬ የሕዝባችን ችግር ኢህአዴግ እንደሚያራግበው
የክልል፣ የቋንቅ፣ የሀይማኖትና የዘር ልዩነት አይደለም፣ ችግሩ ዳር ድንበራችንን አስጠብቆና አንድነታችንን አጠናክሮ የተለመደ አብሮ
የመኖር የፍቅርና የአንድነት ባህሉን አስጠብቆ ከድህነት ማጥ ውስጥ በማውጣት ለተሻለ ሕይወት ሊያበቃን የሚችል ሐዝብ
የመረጠውና የሕዝብን አመኔታ ያገኘ መንግሥት አለማግኘት ነው፡፡ የኢህአዴግ መንግሥት የኢትዮጵያ ሕዝብ ከአያት ቅድመ አያቱ
ጀምሮ የያዘውንና እትብቱ የተቀበረቡትን መሬት በሀይል ነጥቆ ሕዝባችንን እንደፈለገ የሚነቅለውና የሚተክለው አዲስ አይነት
የመንግሠት ጭሰኛ አድርጎታል፡፡ በገጠርም ሆነ በከተማ የሚገኘው መሬት የኢትዮጵያ ሕዝብ ደሙን ያፈሰሰበት ህይወት
የገበረበት አንጡራ ሀብት ሆኖ እያለ የገዥው ፓርቲ መሬት የመንግሥት እንጂ የሕዝብ የግል ሀብት መሆን አይችልም በሚል
ፈሊጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከአባቶቹ የወረሰውን መሬት በኪራይ እንጂ /በጭሰኝነት/ በባለቤትነት በመያዝ ለልጁ እንዳያወርስ፣
እንዳይሸጥና እንዳይለውጥ በአዋጅ ከልክሏል፡፡ በዚህም የተነሳ የኢህአዴግ መንግሥት የመሬትን ፖሊሲ የፖለቲካ ትርፍ
ለማግኘት እየተጠቀመበት ይገኛል፡፡ መሬት ከሀብትም ሁሉ በላይ የሆነ የገበሬው የደምና የአጥንት መስዋዕትነት የተከፈለበት ምትክ
የሌለው ህይወቱ ነው፡፡ ገበሬውም ሆነ ከተሜው ከመኢአድ ጋር ከተጓዝክ የገጠር መሬት በግል ባለበትነት እንዲያዝ ትታገላለህ
ለድልም ትበቃለህ፣ የከተማ ቦታን ከሊዝ ነፃ በማድረግ የምታዝበት አንጡራ ሀብትህ ታደርጋለህ፣
ሕዝብ በከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ወድቆ እያለ በነጻነት እንደፈለገው በመንቀሳቀስ ለአገሩ እድገትና ለሕዝቡም ብልጽግና ይሰራል
ማለት አይቻልም መንግሥትም ያምናል ማለት የሕዝብን እውቀት፣ ጉልበትና ሀብት አስተባብሮ ለአገር ልማት ለማዋል በመጀመሪያ
ደረጃ አንዱን ልጅ ሌላውን የእንጀራ ልጅ አድርጎ የሚገዛ መንግሥት ሳይሆን የአገሪቱን ሕዝብ ያሳተፈ፣ ፍትሀዊ የሆነና
ከሙስናና ከአድልኦ የጸዳ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ፖሊሲ በአስተማማኝ ሁኔታ መመሥረት ሲቻል ነው፡፡
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ይህን ክፍተት በመሙላት የኢትዮጵያን ሕዝብ በአንድነት፣ በእኩልነትና ፍትህ
በተሞላበት ሁኔታ በመምራት ለነጻነት ለማብቃት በመታገል ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም መኢአድ በ1997 በቅንጅት ከሌሎች
ኃይሎች ጋር በተሰለፈበት ወቅት በደረሰበት በደልና ግፍ ተስፋ ሳይቆርጥ ባለው ከፍተኛ ህዝባዊ ተቀባይነት የተነሳ በአሁኑ ሰዓት
በመላው ሀገሪቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቢሮዎችን በመክፈት ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በዕኩልነት በማሳተፍ ላይ ነው፡፡ በዚህ
የአንድነትና የነጻነት ትግል እንቅስቃሴ የሁሉንም ኢትዮጵያውያን መብት ለማስከበር ከሁሉም ጋር ጥብቅ የሆነ ግንኙነት ፈጥሮ
ተስፋ የተጣለበት ሥራ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ በመላ ሀገሪቱ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ፣
ከርዕሰ ከተማ እስከ ቀበሌ ድረስ በመውረድ ህብረተሰቡን በማደራጀትና በማንቃት፣ ህዝቡ ስለሀገሩ አንድነት፣ ነፃነትና
የዲሞክራሲ ፅንሰ ሀሳብ ግንዛቤ እንዲያዳብር በማድግ ከፍተኛ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል፡፡ የፓርቲው እንቅስቃሴ በሀገር
ውስጥ ብቻ የተወሰነ ባለመሆኑ በተለያዩ ምክንያቶችና መንገድ ሀገራቸውን ጥለው በባዕድ ሀገር በስደት የሚኖሩትን
ኢትዮጵያውያን ጭምር ስለሀገራቸውና ህዝባቸው ማድረግ ያለባቸውን ሁሉ ሀላፊነት በመፈጸም የነፃነት ትግሉ ተሳታፊዎች
ከመሆን አልፈው ባለቤት ጭምር እንዲሆኑ አድርጓል፤ በማድግ ላይም ይገኛል፡፡
መኢአድ በዓለም ላይ ባሉ በርካታ ሀገሮች ተሞክሮ ውጤታማነቱ በተረጋገጠው የሌቨራል ዲሞክራሲ ጽንሰ ሀሳብ ላይ የተመሰረተ
የፖለቲካ ፍልስፍና የሚከተል ፓርቲ ነው፡፡ በዚሁ መሠረት መኢአድ ዋና ግቡ በአገራችን ስልጣን በህዝብ እጅ እንዲገባና ባጭር ጊዜ
ውስጥ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት በመገንባት፣ ፍትህና የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ፣ ለህዝባችን ደህንነትና ልማት ዋስትና
ሊሰጥ የሚችል፤ ባጠቃላይ ለህዝብ መብት መከበር የቆመ መንግሥት መመስረት ነው፡፡ የመኢአድ ተልኮ የኢትዮጵያን ሕዝብ
በነፃዊ ዲሞክራሲ መርህ መሰረት በመምራት የስልጣን አመንጭነቱን፤ ባለቤትነቱንና ተቆጣጣሪነቱን በማረጋገጥ
የበለፀገች ጠንካራ ኢትዮጵያን መገንባት ነው፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
አሁንም ሆነ ወደፊት በቆራጥነት፣ በሙሉ ልብና ብሩህ ተስፋ በተሞላበት ሁኔታ እጅ ለእጅ ተያይዘን በሀገራችን ላይ በአንድነት
የነፃነት ችቦ እንደናበራ ከፓርቲህ ከመኢአድ ጐን እንድትሰለፍ ሀገራዊ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
1. የመጀመሪያው ምርጫ የአሸናፊነቱን መንግሥት መመሥረት ነው፡፡
2. ለዜጋና ለሀገር ከፍተኛ አገልግሎት የሚሰጡ ምሁራንን ከሌሎች ፓርቲዎችም ሆነ ግለሰቦች በመንግሥት መዋቅር ውስጥ
ተሳታፊ እንዲሆኑ ይጥራል ነው፡፡
የመኢአድ የፖለቲካ ፍልስፍናና የወደፊት ራዕይ እንደሚከተለው ይሆናል፡፡
1. ፓርቲያችን በምርጫ የበላይነት ሲቀናጅ ሐገራችንን በጋራና በሕብረት ለመገንባት እንዲቻል እንዳስፈላጊነቱ ከአንድ ወይም
ከዚህ በላይ ከሆኑ ዲሞራሲያዊ ከሆኑት ፓርቲዎች ጋር የጥምር መንግሥት ያቋቁማል፡፡
2. ወቅቱን ጠብቆ በሚከናወነው ምርጫ አንድ ሰው አንድ ድምጽ በሚል የሊበራል ዲሞክራሲ መርሀ መሠረት በግለጽ፣ በነጻና
በፍትሐዊ ምርጫ የሕዝቡን የሥልጣን አመንጭነት በባለቤትነትና በተቆጣጣሪነት ለማረጋገጥ መኢአድ የበኩሉን ሁሉ ያደርጎል፡፡
3. ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጐች የተለያዩ እምነቶችና የፖለቲካ አመለካከቶች በነጻነት ማራመድና ልዩነቶቻቸውን አቻችለው መኖር
የሚችሉበት አመቺ ሁኔታን ለመፍጠር መኢአድ የበኩሉን ጥረት ያማርጋል፡፡
4. ሕግ አስፈጻሚ አካል በቀጥታ በሕዝብ በሚመረጥና የሥልጣን ዘመኑ በሕግ በተገደበ ኘሬዝዳንት የሚዋቀርና የመከላከያ ኃይል
ተጠሪነቱ ለኘሬዝዳንቱ እንዲሆን ይደረጋል፡፡ ይሁን እንጂ የመከላከያ ኃይሉ ለፖለቲካ ጉደይ መጠቀሚያ እንዲውል
አይደረግም፡፡
5. የብሔረሰቦች ክልል ያለ ሕዝብ ጥያቄና ያለ ሕዝቡ ውሳኔ /referendum/ የማይቀየር የማይለወጥ ቢሆንም ማንም
ኢትዮጵያዊ በፈለገበት አካባቢ የመኖር፣ የመስራት፣ ሐብት የማፍራት ወዘተ… መብቱ የተጠበቀና የተከበረ እንዲሆን
ይደረጋል፡፡
6. ማንኛውም ሰው በሕይወት የመኖር መብቱ፣ የአካል ደሕንነቱና ነጻነቱ ፍፁም የማይጣስና የማይገሰስ መሆኑን መኢአድ ያምናል፤
ለተግባራዊነቱም ይታገላል፡፡
7. ማንኛዋም ሰው ከሕግ አግባብ ውጭ አይያዝም፣ አይታሰርም፣ አይቀጣም እንዲሁም ሰውነቱም ሆነ የግል ንብረቱ ከሕግ አግባብ
ውጭ አይፈተሽም፣ አይወሰድም፡፡
8. መኢአድ የሌሎች ድርጅቶችን ሕጋዊ ሕልውና የሚያከብር ሲሆን በተለያዩ አስገዳጅ ምክንያቶች በትጥቅ ትግልና በስደት ላይ
የሚገኙ የፖለቲካ ቡድኖችና ሌሎች ወገኖቻችንን ሰላማዊና በሕዝባዊ ፖለቲካ መንገድ መሳተፍ እንዲሳተፉ ሐገራዊ የድርድር
መድረክ እንዲመቻች ሁሉን አቀፍ የሆነ የፖለቲካ ሥርአት እንዲሰፍን የማያቋርጥ ጥረት ያደርጋል፡፡
9. ሊብራል ዲሞክራሲ በሰፈነባቸው የበለፀጉ ሐገሮች መገናኛ ብዙሃን እንደ አራተኛ የመንግሥት ዘርፍ ይቆጠራል፡፡ በኢትዮጵያም
ተመሳሳይ ሁኔታ እንዲፈጠር መኢአድ ከፍተኛ ጥረት ያደርጋል፡፡

The post መኢአድ በወያኔ ሚዲያዎች በኢቢሲ በፋና በዛሚ እንዳያቀርበዉ የተከለከለዉ ጽሑፍ appeared first on Zehabesha Amharic.

የተሽከርካሪ አደጋ መብዛት ያሳሰበው መንግሥት ለባለድርሻዎች ጥሪ አቀረበ

$
0
0

-ባለፉት ስድስት ወራት በአዲስ አበባ ብቻ 260 ሰዎች ሞተዋል

-ከ81 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል

katelo 3ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ የመጣው በተሽከርካሪ አደጋዎች በሰውና በንብረት ላይ የሚያደርሱት ጉዳት እያሳሰበው የመጣው መንግሥት፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር አደጋን በተመለከተ ትኩረት ሰጥቶ ለመሥራት ጥሪ አቀረበ፡፡

የተሽከርካሪ አደጋ ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ከመቅጠፉም በተጨማሪ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖው ከፍተኛ መሆኑን በመጠቆም መንግሥት፣ ኅብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት ተባብረው መሥራት የግድ እንደሚላቸው የፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ደመላሽ ገብረ ሚካኤል አሳስበዋል፡፡

የተሽከርካሪ አደጋ በአዲስ አበባ ወይም በከተሞች ብቻ ሳይሆን፣ በፌዴራል ደረጃ አሳሳቢ እየሆነና በየጊዜው መጠኑ እየጨመረ መሆኑን የጠቆሙት ምክትል ኮሚሽነሩ፣ ሁሉም ተባብሮና ትኩረት ሰጥቶ በመሥራት ችግሩን መቀነስ ካልቻለ አሳሳቢ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ባለንብረቱ፣ አሽከርካሪው፣ ኅብረተሰቡና ትራፊክ ፖሊስ ተባብረው የችግሩን መንስዔ በደንብ በማጥናትና መፍትሔ በመፈለግ፣ ችግሩን መቀነስና ማቆም እንደሚገባ ጠቁመው፣ መንግሥትም በጉዳዩ አሳሳቢነት ላይ ትኩረት ሰጥቶ ለመሥራት ቁርጠኛ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ባለፉት ስድስት ወራት የ260 ሰዎች ሕይወት በተሽከርካሪ አደጋ ማለፉን የጠቆሙት ደግሞ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ ፖሊስ ሕዝብ ግንኙነት ረዳት ባለሙያ፣ ረዳት ኢንስፔክተር አሰፋ መዝገቡ ናቸው፡፡ በስድስት ወራት ውስጥ የ196 ወንዶችና የ64 ሴቶች ሕይወት እንዲያልፍ ያደረገው የተሽከርካሪ አደጋ፣ ከ81 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረትም እንዲወድም ማድረጉንም አስረድተዋል፡፡

አሽከርካሪዎች ራሳቸውን ለመከላከል የሚፈልጉት ትራፊክ ፖሊስ ከሚጥልባቸው ቅጣት እንጂ፣ ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ለመጠበቅ አለመሆኑን የገለጹት ረዳት ኢንስፔክተር አሰፋ፣ ከጥቂት ጨዋና ሕጉ የገባቸው ሕግ አክባሪ አሽከርካሪዎች በስተቀር፣ አብዛኛዎቹ ሕግ ለማክበር ወይም ለሕዝብ አሳቢ የሚመስሉት ትራፊክ ፖሊስ ቆሞ ሲያዩ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

እየደረሰ ያለውን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ ከትራፊክ ፖሊስ በተጨማሪ ዓለም የደረሰባቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም ቁጥጥሩን ማዘመን አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን የተናገሩት ባለሙያው፣ ሲሲቲቪ ካሜራና ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም፣ የትራፊክ ፖሊስ በሌለበት ቦታ ሁሉ ቁጥጥር ማድረግ አማራጭ የሌለው መፍትሔ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በተለይ በቅርብ ጊዜ ወደ አገር ውስጥ የገባው የቻይና ሥሪት የሆነው ሲኖትራክ የጭነት ተሽከርካሪ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ፣ ፌዴራል ትራንስፖርት ባለሥልጣን ልዩ የቴክኒክ ቡድን በማቋቋም የችግሩን መንስዔ ለማጥናት በዝግጅት ላይ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ግን ባለሥልጣኑ የያዘውን አቅጣጫ በመቃወም አስተያየታቸውን ለሪፖርተር ሰጥተዋል፡፡

ተሽከርካሪው (ሲኖትራክ) በራሱ ምንም ዓይነት ችግር እንደሌለበት የሚናገሩት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ በኢትዮጵያ በተለይ አሁን እየተሠሩ ባሉ የመንገድ ግንባታዎች ላይ የተሰማሩ በርካታ ሲኖትራክ ተሽከርካሪዎች፣ በአንዳንድ ብቃት ባላቸው ኢትዮጵያውያን አሽከርካሪዎችና ቻይናውያን በአግባቡ እየተገለገሉበት ነው ብለው፣ ተሽከርካሪው ካለው ጉልበት የተነሳ ለሥራው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ተሽከርካሪው በቴክኒክም ሆነ በይዘት በኩል ችግር እንደሌለበት ተናግረዋል፡፡ ነገር ግን በተቃራኒው በየዕለቱ በተለይ በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ የተሽከርካሪ አደጋ እየደረሰ ያለው በሲኖትራክ መሆኑን የሚናገሩት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ ‹‹ይኼ የሚያሳየው የተሽከርካሪውን ሳይሆን የአሽከርካሪዎችን ችግር መሆኑን ነው፤›› ሲሉ ችግሩ የአሽከርካሪዎች መሆኑን ያስረዳሉ፡፡

አንድ አሽከርካሪ ሁለተኛ የመንጃ ፈቃድ (ቀላል አውቶሞቢሎችን ለማሽከርከር የሚያስችል) ለማውጣት የትራፊክ ደንቦችንና ምልክቶችን ከማጥናቱም በተጨማሪ፣ የማሽከርከር ብቃቱን በደንብ የሚለካበት ሥልጠና ወስዶ፣ ሁለቴና ከዚያም በላይ በተግባር ፈተና ወድቆ፣ በደንብ ከሠለጠነ በኋላ ያገኝ እንደነበር አስተያየት ሰጪዎቹ አስታውሰዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ግን አንድ አሽከርካሪ ራሱ ካልፈራ በስተቀር በአንድ ጊዜ አምስተኛ መንጃ ፈቃድ የሚያገኝበት ዕድል እንደተፈጠረለት ጠቁመው፣ ‹‹እንኳን ሲኖትራክን ቀርቶ ቀላል የቤት አውቶሞቢልን የማሽከርከር ብቃት አይኖረውም፤›› ሲሉ፣ የችግሩ መንስዔ የአሽከርካሪዎች ብቃት ማነስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የተሽከርካሪውን የቴክኒክ ብቃት ለማስጠናት ኮሚቴ በማቋቋምና የቴክኖሎጂ ውጤት የሆነውን ተሽከርካሪ ለማጥናት ከማሰብ ይልቅ የአሽከርካሪዎቹን የማሽከርከር ብቃት፣ የመንጃ ፈቃድ ትምህርት ቤቶች የማሠልጠን ብቃት፣ የትራፊክ ፖሊሶች የመቆጣጠር ብቃትና የመንገዶችን ብቃት ማጥናቱ የተሻለ እንደሚሆን መክረዋል፡፡

ረዳት ኢንስፔክተር አሰፋ መዝገቡና ረዳት ኮሚሽነር ደመላሽ ገብረ ሚካኤልም አስተያየት ከሰጡት የኅብረተሰብ አካሎች ጋር ተመሳሳይነት ያለው አስተያየት በተለይ በአሽከርካሪዎች ብቃትና በትራፊክ ፖሊሶች ቁጥጥር ላይ አስተያየታቸውን ሰንዝረዋል፡፡ በአፍሪካ የተሽከርካሪዎች ብዛት ከዓለም ሁለት በመቶ የሚሆነውን የሚሸፍን ቢሆንም፣ በአኅጉሪቱ የሚከሰተው አደጋ ግን የ20 በመቶ ድርሻ እንዳለው ጥናቶች እንደሚያመለክቱ አስተያየት ሰጪዎቹ ጠቁመዋል፡፡ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ አገሮች ችግሩ የባሰ ስለሚሆን መንግሥት፣ ኅብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት ተባብረው በመሥራት ችግሩን ማጥፋት ባይችሉ እንኳን መቀነስ ተገቢ መሆኑን አክለዋል፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

The post የተሽከርካሪ አደጋ መብዛት ያሳሰበው መንግሥት ለባለድርሻዎች ጥሪ አቀረበ appeared first on Zehabesha Amharic.

ሶስት ሚሊየን ብር የሚጠጋ ወጭ የወጣበት ድልድይ የጥራት ችግር አለበት ተባለ

$
0
0

downloadየካቲት ፳፮(ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአባይ ወንዝ ላይ የተሰራዉ 108 ሜትር ርዝመት እና አንድ ነጥብ ስድስት ሜትር ስፋት ያለው ተንጠልጣይ ድልድይ በሃገሪቱ ብቸኛዉ የተንጠልጣይ ድልድይ በመስራት በሚታወቀው ሄልቬታስ ሲዊዝ ኢንተርኮኦፕሬሽን በተሰኘ መንግስታዊ ባልሆነ ድርጅት ባለፈው ታህሳስ ወር መጨረሻ በይፋ ተመርቆ ስራ ቢጀምርም፣ በምረቃው ስነስርዓት የተገኙ ባለሙያዎች ድልድዩ የጥራት ችግር እንዳለበት መናገራቸው ነዋሪዎችንና በቦታው ተገኙ አመራሮችን አስደንግጧል፡፡

በአማራ ክልል ገጠር መንገድ ስራዎች ድርጅት የቁጥጥርና ክትትል ኬዝ ቲም ባለሙያ የሆኑት አቶ ይገርማል ታምር በዝርዝር ያቀረቡት የጥራት ችግር በምረቃ ስነስርዓቱ ለታደሙ የክልል እና የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ የበጎ አድራጎት ድርጅቱ ኃለፊዎች፣ ግንባታውን በኃላፊነት የሰራው ባለሙያ እና የአካባቢውን ነዋሪዎችን ያስደነገጠ እንደነበር በምረቃው ስነስርዓት የተገኙ ታዛቢዎች ተናግረዋል፡፡

40 በመቶ በሄልቬታስ ፤60 በመቶዉ ደግሞ ከዓለም ባንክ የግብርና እድገት ፕሮግራም በተገኘ ገንዘብ ወጭዉ የተሸፈነው ይህ ድልድይ ለሃምሳ አመታት እንዲያገለግል ታስቦ የተሰራ ቢሆንም የተሰራበት የድንጋይ አይነት፣የውሃ አጠጣጡ እና ገመዶችን ወጥሮ የያዘው የግንባታ አካል ስጋት ያለበት መሆኑን ባለሙያው ተናግረዋል፡፡

የዳስራ ማርያም እና የጭስ አባይ እንዲሁም በደቡብ ጎንደር ዞን ደግሞ የደራ ወረዳ የተወሰኑ የገጠር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደሮችን የዘመናት ጥያቄን የፈታ ሁኗል የተባለለት ታንኳ በር ተንጠልጣይ ድልድይ እንዲሰራ ላለፉት ሁለት ዓመታት አርሶ አደሮች በተደጋጋሚ ለሚመለከተዉ አካል ጥያቄ ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡

ሄልቬታስ ስዊዝ ኢንተርኮርፕሬሽን የተባለው የግብረ ሰናይ ድርጅት በክልሉ በተለያዩ ቦታዎች የሚሰራቸውን ተንጠልጣይ ድልድዮች ስራ በብቸኝነትና ማንም ተቆጣጣሪ በሌለበት ሁኔታ እንደሚሰራና ማኔጅመንቱም በአንድ አካባቢ ሰዎች ብቻ የተያዘ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ድርጅቱ በአምስት ክልሎች ከስልሳ በላይ ተንጠልጣይ ድልድዮችን እንደሰራ በእለቱ የምረቃ ስነስረአት ላይ ተገልጿል፡፡

Source:: Ethsat

The post ሶስት ሚሊየን ብር የሚጠጋ ወጭ የወጣበት ድልድይ የጥራት ችግር አለበት ተባለ appeared first on Zehabesha Amharic.

ማስተርስ/ዶክተሬት እንደ መለዋወጫ እቃ! (ታሪኩ አባዳማ)

$
0
0

ታሪኩ አባዳማ | የካቲት 2007

ልጄ አስራ ሁለተኛ ክፍል ስለጨረሰ የደስታዬ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ… የሚል ግብዣ ደርሷችሁ አያውቅም? እናንተም ፋሽኮ ቪኖ ወይንም እናትና ልጅ አረቄ ይዛችሁ ድግሱን ለማድመቅ ሳትሄዱ አልቀራችሁም – የዚያን ዕለት ጎረምሶቹ የቀለጠ ፓርቲ ደግሰው እስኪነጋ ይጨፍራሉ አሉ… ይህስ ይሁን።Fake-Indian-degrees-abound

ድህረ ምረቃ ፕሮግራም ላይ መሆኑን አንድም ቀን ሲናገር ሰምታችሁ የማታውቁት በቅርብ የምታውቁት ሰው ፣ እንዲያውም በመደበኛ ትምህርት ከስንተኛ ክፍል ነበር? አቋርጦ ወደ ሄደበት ሄዶ (ጫካ ወይንም ምርኮ) ግን የዛሬ ‘ሹም’ ‘የማስተርስ ፣ ዶክትሬት ዲግሬዬ በፖሰታ ስለደረሰኝ የደስታዬ ተካፋይ እንድትሆን ብሎ ቢጠራችሁስ? ይኼ ሰው ድሮ ትምህርት ቤት የተመዘገበበት ስም ሌላ ነበር… አሁን ደግሞ አዲስ ስም ብቻ ሳይሆን አዲስ ማዕረግ ፣ አዲስ ቤት ፣ አዲስ መኪና… ምኑ ቅጡ… ባናቱ ላይ ዲግሪ ሸምቶበታል።

ይድረስ ለተከበሩ… አስፈላጊውን ክፍያ ስላጠናቀቁ የ ማስተርስ ዲግሪዎን አያይዘን ልከናል – ለዶክተሬት ዲግሪዎ ተመልሰው እንደሚመጡ ተስፋ እናደርጋለን – የዋጋ ቅናሽም እናደርግሎታለን – ስለ ደንበኝነታችን ሲሉ አገልግሎታችንን ለስራ ባልደረቦችዎ እንዲያስተዋውቁልን ትብብሮን እንጠይቃለን – ለዚህም ተገቢውን ወሮታ እንከፍላለን – ያስታውሱ ‘ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ’ – ሴንቸሪ ዩንቨርሲቲ

ታዲያ እርሶም ለምርቃቱ ተጋብዘዋል – በተጠራው ድግስ ላይ ‘…ሁለተኛ ደረጃ ትምህርትህን የት ነበር የጨረስከው ፣ ማትሪክ ውጤትህስ ስንት ነበር ፣ የመጀመሪያው ዲግሪህስ… ያጠናኸው ፣ የተመራመርከው እና መቸ ያዘጋጀኸው መመሪቂያ ቴሲስ ነው ለዚህ ያበቃህ?…’ ብላችሁ ትጠይቃላችሁ ወይስ ድግሱን ተቋድሳችሁ …እንኳን ለዚህ አበቃህ ብላችሁ መርቃችሁ ትመለሳላችሁ?

አነሳስቶ ላስጀመረን ፣ አስጀምሮ ላስጨረሰን ተብሎ ባደባባይ በግልፅ ሳይተያዩ ማስትሬት እና ፒኤችዲ እንደ መለዋወጫ እቃ ‘…ኦን ላይን ኦርደር…’ ማድረግ የወቅቱ የወያኔ ሹማምንት ልዩ መታወቂያ መሆኑን ስናይ ‘ኦ ዲግሪ ሆይ ከስምሽ ጀርባ ስንት ደደብ መሸገ’ እንድንል ያስገድደናል። ባንድ ጀምበር ሚሊየነር ፣ ባንድ ጀምበር ጄነራል እናም ባንድ ጀምበር ዶክተር እገሌ መባል ወያኔአዊ ተፈጥሮ ያመጣብን በሽታ ነው። እነኝህ ሰዎች በየመስኩ በሚፈጥሩት ስፍር ቁጥር የሌለው የተዛባና ህገ ወጥ አሰራር ጉዳቱ ውሎ አድሮ አገሪቱ ላይ በሁለንተናዊ መልኩ እየተንፀባረቀ መሆኑን ለመናገር የሚያስቸግር አይመሰለኝም። አዲሱ ሚሊየነር በሙስና እና ነጠቃ ላይ የተገነባ መሆኑ ፣ ጄነራሉ ችግር ሁሉ የሚፈታው በጠመንጃ ብቻ ነው ሲል የቁጩ ማስተርስ እና ዶክተርም የነሲብ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ መፍትሔ ሲያረቅ ሲያማክር… እንዲያው ተያይዞ ገደል መግባት መሆኑ ቁልጭ ብሎ አይታያችሁም?

‘…ለኢህአዴግ ታማኝ እስከሆነ ድረስ ማይም እንኳ ሚኒስትር መሆን ይችላል…’ ያለው ማን ነበር? ሙት ወቃሽ እንዳልሆን ብዬ እንጂ ይኼ ድኩም ራዕይ የተሰነቀው ገና ከጠዋቱ እንደነበር አትዘንጉ ለማለት ነው። የአሳ ግማቱ ከወደ አናቱ!!

አንኳንስ ዶክተሬት ስምንተኛ ክፍል ሲጨርሱ ካባ ለብሶ ፎቶ መነሳት ፣ የምርቃት ቀን ደግሞ ሽክ ባለ ልብስ ፣ ባጌጠ አደራሽ ፣ ሞቅ ደመቅ ባለ ስነስርዓት ዘመኑን መቋጨት እዚህ በምእራቡ አለም ጭምር የተለመደ ነው። ከዩንቨርሲቲ ሲመረቁ ደግሞ ስርዓቱ ለየት ይላል – ይኼ ሁሉ የሚደረገው ግን አንድም ትምህርት በአግባቡ የተሰጠ ለመሆኑ ይፋዊ ማረጋገጫ ለመስጠት ሲሆን – ሽፍንፍን ፣ ድብቅብቅ ተመርቂያለሁ ማለት ባካዳሚው አለም ሆነ በህብረተሰቡ ውስጥ ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ መሆኑን ለማሳየት ጭምር ነው። ይህን ስል በወያኔ ተቋማት አደባባይ የተመረቀ ሁሉ ብቃቱ ተረጋግጧል ማለቴ አይደለም።

ወያኔ ሁሉንም ዘዴ እንደ አስፈላጊነቱ ይጠቀምበታል። ከገበያ መሸመት ያለባቸው ሹሞች በጀት ተይዞላቸዋል – በተጠረቡ ቤቶች ውለው አድረው ‘የሚመረቁ’ ደግሞ አሉ… ከሲቪል ኢንሲቲትዩት… ከዚህ ሰፈር ከዚያ ሰፈር ኮሌጅ… ከዚህ ከዚያ ህዝቦች ዩንቨርሲቲ… ኮብል ስቶን ጠራቢ ምሩቃን ከታማኝ የወያኔ ካድሬ ምሩቃን ጋር ተማክረው ስለጉዳዩ የበለጠ ሊነግሩን ይችላሉ።

በምዕራቡ የትምህርት አለም ግን ልጆቻችሁን አስተምረን እዚህ አድርሰናል ፣ አዘጋጅተናል ፤ ኑ ተረከቡን የሚል ጥሪ ለወላጆች ሲቀርብ – ወጣቶቹ ለመጪው የከፍተኛ ትምህርት ዘመን ወይንም ለላቀ ሀላፊነት መዘጋጀታቸውን ለማብሰር ብቻ ሳይሆን ጠንክረው በጥሩ ውጤት ያጠናቀቁትን በአርአያነት በአደባባይ በመሸለም ሌሎችም እንዲተጉ ለማበረታታት ጭምር ነው። ይህም የሚደረገው አለምክንያት አይደለም።

የትምህርት ደረጃ የማይዛነፍ ራሱን የቻለ እርከን ፣ አድማስ እና ጥልቀት አለው – በትምህርት ገበታ የተወሰነ አመታት ማሳለፍ በራሱ የተጠና ፣ የተወጠነ ግብአት ያለው መሆኑንም መረዳት አያዳግትም። እያንዳንዱ እርከን ከዕድሜና የአይምሮ መጎልመስ ጋር ተቀናጅቶ ፣ በጥንቃቄ ተመጥኖ እየተለካ ዕውቀት የመመገብ ዘዴ ተዘርግቷል – መደመር እና መቀነስ ብለው ሳይጀምሩ ፣ ረጅሙን የሂሳብ ጎዳና ሳይጓዙ ካልኩለስ ስሌት ውስጥ መግባት እንደማይቻል ሁሉ ወግ ያለው መደበኛ ትምህርት በተገቢው መንገድ ሳይታለፍ ባቋራጭ ማስተርስ እና ፒኤችዲ አገኘሁ ማለት ራስን ከማጃጃል አልፎ ጦሱ የት እየለሌ ነው።

የረባ ዕውቀት ሳይጨብጡ ድሀ አገርን ያህል ለመምራት መድፈር ፣ ‘ድህነትን ታሪክ እናደርጋለን’ ከሚል ባዶ መፈክር የዘለለ ፋይዳ የለውም – ውጤቱ ከባዶ ጣሳ ወደ ተቀደደ ጣሳ ውሀ አገላብጥኩ እንደ ማለት ያህል ነው። ይሄም ባዶ ያም ባዶ – ከባዶ ለባዶ!! Blank of blank ይሉታል ፈረንጆቹ።

በመጀመሪያ ዲግሪ ለመመረቅ አራት ዓመታት የሚፈጀው በሚሰጡት ኮርሶች የሚገኘው ዕውቀት ብቻውን ያን ያህል ዘመን ይፈጃል ተብሎ አይመስለኝም። ተማሪው አራት ዓመታት በዚያ የእውቀት ማዕከል ሲመላለስ ከመደበኛው ትምህርት ሌላ ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊ ፣ አለም አቀፋዊ እና ቤተሰባዊ ልምድ እና እውቀት አጣምሮ በመቅሰም አይምሮውን ያጎለምሳል። ካንድ ደረጃ ወደሚቀጥለው ለመሻገር የትናንቱ ለዛሬው ፣ የዛሬው ለነገው የሚያወርሱት መሰረት እጅግ አስፈላጊ ናቸው። መደበኛ ትምህርት ወደ ስራ አለም ሲሰማሩ ሀላፊነትን በብቃት ለመወጣት የሚያስችል ስንቅ መደቆሻ አምባ ነው። በወጉ ሳይሰንቁ ሩቅ ለመጓዝ አይታሰብም ፣ በድፍረት የመጣው ይምጣ ብሎ መጓዝ ይቻል ይሆናል ውጤቱ ግን ባዶ መፈክር እያመረቱ ማደናገር ይሆናል – ከባዶ ጭንቅላት የሚመነጩ መፈክሮች መሬት ላይ ካለው ውነት ጋር የሚጣረሱ ለመሆናቸው ያለፉትን 23 ዓመታት ብቻ ማስተዋል ይበቃል – በቀን ሶስት ጊዜ ትበላለህ አይነት!!

ትምህርት እውቀት ነው ፣ እውቀት ደግሞ ሀይል ነው። የትምህርት ማዕረግ ሸምቶ ባልሰለጠኑበት ደረጃ እና ብቃት ሀላፊነት ላይ መቀመጥ ‘ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት ዳገት ላይ ይለግማል’ እንዲሉ ፈታኙን የህብረተሰብ ሁለንተናዊ ችግሮች ለመጋፈጥ እና ለማቃለል ከቶውንም ማጠፊያው ይቸግራል። ይህንነም በተጨባጭ እያየነው ነው – እቅድ ተነደፈ ተብሎ ወረቀት ላይ የሚለቀልቁት ቅዠት ከዕውቀት ማነስ የሚመነጭ መደናበር ነው። በየዘመኑ ማክተሚያ ‘እቅዳችን ያልተሳካው …’ 99 ሰበብ መደርደር።

በቅርቡ ይፋ ሆነው ባነበብናቸው የምርመራ ዘገባዎች እንደተገነዘብነው አገራችን ከቶውንም የዩንቨርሲቲ ደጃፍ መርገጥ ቀርቶ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በወጉ ያላጠናቀቁ ባለስልጣናት የተሸከሙትን የሙያ ማረጋገጫ ምስክር ሰነድ እያየን ነው። ሳይማሩ የጠመጠሙ ዳውላ ሹማምንት እየበረከቱ መሆኑን በማስረጃ ተደግፎ የቀረበው ዘገባ አረጋግጧል። ይኼ ዜና አሳፋሪነቱ ድርጊቱን ለፈፀሙት ቱባ ባለስልጣናት ብቻ ሳይሆን እነዚህን ታቅፎ ተመርኩዞ አገር እየገዛ ላለው የወያኔ ስርአት ጭምር ነው።

ወያኔ ግን ሀፍረት ያውቃል እንዴ?

ይችን አስተያየት ለመክተብ ያነሳሳኝ ዋና ምክንያት ድንቅ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ባቀረበው በዚህ ጥናታዊ ዘገባ ከተጋለጡት (ቅሌት ከተከናነቡት ብል ይሻላል) ግለሰቦች አንዱ አቶ ቆስጠንጢኖስን ባንድ አገጣሚ የማውቀው በመሆኑ ነው። ሰውዬውን ያገኘሁት እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር 1971 – 72 አብረን ማዕከላዊ ብሎም ከርቸሌ በቆየንባቸው የእስር ዘመናት ነበር። ያንን የእስር ዘመን በሚመለከት በቃለ መጠይቅ የተናገረውንም ሰምቻለሁ… ቆስጤ ያው እንደ ጥንቱ ነው – ሲናገር ሳግ አያንቀውም – የሴንቸሪው ዶክተሬት በባህሪው ላይ ለውጥ አላመጣም።

በሰኔ ወር 1971 ዓም በደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢ ደርግን የሚያሰጋ አንዳች ህቡዕ እንቅስቃሴ በደህንነት መስሪያ ቤት የተደረሰበት መሆኑ ይወራል። በዚህ እንቅስቃሴ ተሳትፈዋል የተባሉ አስራ ዘጠኝ ያህል የጂጌሳ እና ሰንቀሌ እንጨት መሰንጠቂያ ወዛደሮች (በደን ልማት ባለስልጣን ስር የነበሩ ፋብሪካዎች ናቸው) የፋብሪካዎቹ ዋና ስራ አስኪያጅ አለማየሁ ዘውዴ እንዲሁም በሻሸመኔ እና አካባቢው በልዩ ልዩ መስክ የተሰማራን ግለሰቦች በአካባቢው የደርግ ተጠሪ ኮሎኔል አባተ መርሻ አዝማችነት ከያለንበት ታድነን ደቡብ ጦር ሰፈር በሚገኝ እስር ቤት ገባን። በማግስቱ በከፍተኛ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች አጀብ አዲስ አበባ ተጓጉዘን ማዕከላዊ እስር ቤት እንታጎራለን። የተከሰስንበት ጉዳይ መንግስትን በወታደራዊ ሀይል ለመገልበጥ ዝግጅት ማድረግ የሚል ነበር። ‘… ጦር መሳሪያ አከማችታችሁዋል ፣ ወታደራዊ ስልጠና እየወሰዳችሁ ነው..’ ይላል የክሱ ቻርጅ። ከታሰርነው መካከል አንድም ወታደር የለም – እርግጥ ነው እሳት ከሌለ ጭስ የለም… እሳቱ ግን የነደደው ሌላ ሩቅ ሩቅ ሰፈር ነበር… ዝርዝሩ ወደ ሌላ ታሪክ ስለሚወስደን ለጊዜው እዘለዋለሁ።

ይህ በንዲህ እንዳለ አዲስ አበባ የደን ልማት ሰራተኞች ማህበር ሊቀመንበር ሀይሉ ዳኜ ተይዞ በኛ የክስ ሰነድ ተካተተ ፤ ብዙም ሳይቆይ ቀንደኛው ተጠርጣሪ ቆስጠንጢኖስ በረኼ ነው በሚል እሱም ተይዞ መጣ።

ቆስጤን በዝና እንጂ እስከዚያ ድረስ በአካል አላውቀውም ነበር… ደን ልማት ውስጥ ማለፊያ ስልጣን ያለው ሰው ሲሆን ተወዳጅ ተክለሰውነትም ነበረው… ረጋ ብሎ መናገር… ግን ሳያቋርጥ የመናገር ችሎታ አለው። ምንም ርዕስ ስጡት ቆስጤ እንደ ልዩ ባለሙያ ይተነትነዋል ፣ ያብራራዋል… ልዩ ተስጥኦ ነው። ታዲያ ከሚናገራቸው ነገሮች ውስጥ አብላጫው መጨበጫ መያዣ የሌለው ነገር ነበር… የቱ ውነት የቱ ውሸት መሆኑን እንኳ ለመለየት ይቸግራል። ያኔ እኔ ገና የ12ኛ ክፍል የህብረተሰብ ትምህርት ተማሪ ስለነበርኩ ቆስጤ የሚተነትነው የፊዚክስ ንድፈ ሀሳብ ሚስጥር ሆኖብኛል። በዚህ የተነሳ በጣም አደንቀዋለሁ – በብዙሀኑ እስረኛ ዘንድ በዚያን ዘመን ማዕከላዊ ከነበሩ ምሁራን እንደ አንዱ ይቆጠር ይከበርም ነበር።

አወይ ማዕከላዊ! እኛ በታሰርንበር ዘመን እስር ቤቱ ተጨናንቆ እና ገንፍሎ ከቤት ውጭ መተላለፊያው ላይ ሰሌን ዘርግተን መተኛት ነበረብን። ማዕከላዊ ስንገባ እነ ጋሼ አሰፋ ጫቦ በጨለማ ቤት እንደታሰሩ ነው ፣ እኔ የደረሰኝ ላይኛው ግቢ 8 ቁጥር ሲሆን ብዙ ሰዎችን የመተዋወቅ ዕድል አጋጥሞኛል። እዚህ አሜሪካ ባለፈው ዓመት ዋይት ሀውስ ተጋብዞ ከፕሬዘደንት ኦባማ ልዩ ክብር የተቸረው ሳይንቲስቱ ዶር ሰለሞን ቢልልኝ የ8 ቁጥር ባልደረባዬ እንደነበረም አስታውሳለሁ።

የቼዝ ጨዋታ ስልት አስተምሮ ለውድድር እንድሰለፍ ያበቃኝ ሙባረክ ሸሪፍ (የሸሪፍ ላውንደሪ ባለቤት ልጅ) ከዚያው ከ8 ቁጥር ነበር ሌሊት ሌላ ክፍል ታስረው ከነበሩ ጓዶቹ ጋር ተወስዶ የተረሸነው (ከብርሀነመስቀል ረዳ ጋር ከጫካ የተያዙ ወጣቶች ናቸው)። እስከዛሬ ድረስ በቤተሰብ ደረጃ ግነኙነታችን ተጠብቆ የሚገኝ የዚያን ጊዜ የ8 ቁጥር እስረኛ ባልደረባዬ በቀለ ተፈራ ዛሬ ከነቤተሰቡ ጀርመን አገር ይኖራል… አዲስ አበባ ታዋቂ ኮማሪቶች ፔጆ 504 ወርቅና ውድ ጌጣ ጌጥ እየሸመተ ሲያንቆጠቁጣቸው የነበረው የመንግስት እርሻ ልማት ሀላፊ የነበረውን በርሔ ተመልሶንስ ታስታውሱታላችሁ? እሱም 8 ቁጥር ነበር። ስንቱ ይነገራል።

አለም በቃኝ ሲወስዱን ደግሞ የልጅነት ጓደኛዬን የሽመልስ ኦላና ታናናሽ ወንድሞች ሀይለልዑል እና ዳኜ አገኘሁዋቸው። ሽመልስ ኦላና አምቦ አካባቢ በግፍ መገደሉ ሳይበቃ ደርግ መላ ቤተሰቡን ለረጅም ጊዜ በእስር አሰቃይቷል ፣ ቤት ንብረታቸውን ቀምቶ ባዶ አስቀርቷቸዋል። አባቱ አንጋፋው ኦቦ ኦላና ባቲ በወያኔ ዘምንም ቢሆን ከመንገላታታት አላመለጡም። አንዳንድ ቤተሰብ ላይ የወረደውን ግፍ ሲያስቡት ይዘገንናል።

ከርቸሌም ቢሆን በየቤቱ ከታጎረው እስረኛ ሌላ አለም በቃኝ ክልል ሜዳው ላይ የላስቲክ ጎጆ ቀይሶ የሚያድረው ቁጥሩ እጅግ ብዙ ነበር። የመጀመሪያ ቀን አዳሬን ያደረኩት የ8 ቁጥር ባልደረባዬ ከነበረው ከመሐመድ ኢዛም ጋር ሲሆን – (መቸም 8 ቁጥር ኖሮ መሀመድ ኢዛምን የሚዘነጋው ያለ አይመስለኝም)። ተናግሮ የሚያስቅ ፣ ፈገግታ ከፊቱ የማይለይ ፣ ጨርሶ እስር ቤት መሆኑን ለመዘንጋት እና ሌሎችም እንዲዘነጉ ለማድረግ የነበረው ተሰጥኦ የሚገርም ነው። የኮሜርስ ምሩቅ እና የባንክ ሰራተኛ ነበር – ታዲያ የዚያን ዕለት ሜዳ ላይ አነጣጥፈን ከመተኛታችን ዝናም መንጠባጠብ ይጀምራል – መጠለያ የሚሉት ነገር የለም ምክንያቱም ቤት ውስጥ የሚተኙት በሙሉ ተቆልፎባቸዋል – መሀል ላይ ያለው በረንዳ ለጠጠር መወርወሪያ የሚሆን ክፍተት አንኳን የለውም – እስረኛው እንደ ርስቱ የሚቆጥረው የመኝታ መደብ አጨናንቆታል። እናማ ከዝናም መሸሻ ቦታ የለም። መሐመድ ኢዛም ግን እንዲህ አለኝ ‘አይዞህ አትስጋ ዝናም በአስማት የማቆም ችሎታ አለኝ… ብቻ የሚሆነውን ጠብቅ’ ሲል በማይገባኝ ቋንቋ መለፍለፍ ጀመረ…. ውነትም አስገምግሞ የመጣው ዝናብ በመንጠባጠብ ቀስ በቀስ በረደ – እኛም አንቀላፋን። ሁዋላ ውጭ ከመተኛት የታደጉኝ የሸመልስ ወንድሞች ናቸው።

ብዙ ትዝታ ያተረፍንበት ዘመን። … ወደ ቆስጤ ልመልሳችሁ።

እንዳልኩት በዚህ ጉዳይ ላይ ለመፃፍ ያነሳሳኝ የቆስጤ ነገር ነው። ትምህርቱን ከአዲስ አበባ ዪንቨርሲቲ ያውም በአፄው ዘመን ያጠናቀቀ ማለፊያ ጭንቅላት የነበረው ቆስጤ ምን ሲያደርግ የዩንቨርሲቲ ደጃፍ ረግጠው ከማያውቁ እነ አባዱላ ገመዳ ተርታ የሚያስልፈው ድርጊት እንደ ፈፀመ ሳስበው ይገርመኛል? በውነቱ በፖለቲካ እምነቱ ከወያኔ ጎን ቢሰለፍ ፣ እሱም እንደነሱ የዘር ሐረግ መዝዞ ይህን እና ያንን ስልጣን ቢጨብጥ ለምን ይህን አደረክ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ላይሆን ይችላል – ሰልጣን በዘር መስፈርት እንደ ቆሎ በሚታደልበት ዘመን እሱም ከዚያ ሰልፍ ውስጥ መግባቱ ቢያስቆጭም ትምህርትን ያክል ታላቅ ነገር የዘረኞች ማላገጫ ሲደረግ ግን ለምን እሱ ራሱ ግንባር ቀደም አድራጊ ፈፃሚ ሆነ? ውሻ በቀደደው…

ቆስጤ ይበልጥ ትዝ የሚለኝ ከርቸሌ ወደኛ ክፍል ተዳብሎ መኖር ከጀመረ በሁዋላ የሆነው አጋጣሚ ነበር። ዘመኑ 1972 ወሩ ትዝ አይለኝም ለሆነ የእስልምና ብሔራዊ በአል ቀን ወህኒ ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ ጫት በይፋ እንዲገባ ይፈቀዳል – በዕለቱ ከውጭ በገባልን ጫት ምርቃና ሞቅ ደመቅ ያለ ውይይት ተከፍቶ ብዙም ሳይቆይ መድረኩ ለቆስጤ ይሰጠዋል። የንግግሩ ርዕስ ስለ ፊዚክስ የትምህርት መስክ ሲሆን በወቅቱ በመስኩ ስለተገኙ አዳዲስ ግኝቶች ምን ሊነግረን እንደሚችል ከቤቱ ጥያቄ ቀረበ። ቆስጤ ትንተናውን ጀመረ – ያኔ እኔ የ12ኛ ክፍል የሶሻል ሳይንስ ተማሪ ስለነበርኩ ስለፊዚክስ ብዙም ዝንባሌ አልነበረኝም። ይሁንና ቆስጤ ከሚሰጠው ትንታኔ በተለይ ስለ ህዋ ምርምር የተደረሰበትን ጭብጥ ሲያብራራ ሁላችንም ፈዘን በተመስጦ ‘በምርቃና’ መንፈስ እንከታተለው ነበር። አገላለፁ ቴክኒካል ተርም የሚበዛበት በመሆኑ ይመስለኛል አብዛኛው ነገር አልገባኝም – ሁላችንም ግን ባድናቆት ተከታትለነዋል። ያን ያህል ራሱን መግለፅ የሚችል ሰው ፣ የመጀመሪያ ዲግሪውን አንቱ ከተባለው የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ለፍቶ ደክሞ ያገኘ ሰው እንዴት መደበኛ ትምህርታቸውን በወጉ እንኳን ካላገባደዱት እነ አባዱላ ገመዳ ተራ ለመሰለፍ መረጠ? መልሱን በጨዋ ደንብ ሊሰጠን የሚችለው ቆስጤ ብቻ ነው።

ዛሬ አለም ያለበትን የቴክኖሎጂ ዕድገት ደረጃ ስናይ የሰውን ዘር ለዚህ ምጥቀት ያበቁ ሳይንቲስቶች በየዘመኑ ተጠበው በምርምር ባስገኙት ውጤት መሆኑ ግልፅ ነው። ከጥንት እስከ አሁን ደረጃ በደረጃ እየበለፀገ እየዳበረ ዕውቀት ይበልጥ እየረቀቅ ብሎም እያንዳንዱ መስክ ዳብሮ ልዩ የሙያ ዘርፍ መፍጠር አስፈላጊ የሆነበት ዘመን ላይ ነን። የስራ ክፍፍል ለብቃት መጎልበት አይነተኛ መሣሪያ እንደሆነ ሁሉ ካንድ የጠቅላላ ዕውቀት ዘርፍ ወደ ሰፔሸላይዜሽን ሽግግር የሚደረገው ያው ብቃትን ለማጎልበት ሲባል ነው። ይኼ ደግሞ በድህረ ምርቃ የትምህርት ዘርፍ ስልጠና እና ምርምር በማድረግ የሚጨበጥ ውጤት ነው። ታዲያ ከምድር ተነስቶ የድህረ ምረቃ ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት መሸመት ባጠቃላይ ባገሪቱ እና በተለይ በትምህርት ገበያ ዘንድ ያለውን ሚዛን ምን ያህል እንደሚያዛባው የሚጠፋው ማነው? ቆስጤ ኦን ላይን ኦርደር የተደረገ ዲግሪ መሸመት ትምህርትን በቁሙ ለመግደል ከተሰለፉ ማይማን ተርታ እንደሚያሰልፈው እንዴት ጠፋው?

አገርን ለመግደል የትምህርት ስርዓቱን መግደል ፣ የትምህርትን ብቃት ዋጋ ማሳጣት እና ስልጣንና ሀላፊነት ዘር መዝዞ ለተጠጋ ሆዳም ማስታቀፍ – ይኼ ነው ከወያኔ አንቀፅ 39 ያተረፍነው – ትምህርት እና በተግባር የተፈተነ የሙያ ብቃት ሳይሆን ከዚህ ከዚያ ዘር መምጣት… እናም ስለ ዲግሪው ሴንቸሪ ዩንቨርሲቲ ይጨነቅበት።

ዶክተሬት በፖሰታ ልኬልሀለሁ
የድሮ ስምህን ደልዠዋለሁ…. አጅሬ ዶክ…

The post ማስተርስ/ዶክተሬት እንደ መለዋወጫ እቃ! (ታሪኩ አባዳማ) appeared first on Zehabesha Amharic.

አፈረች ዲያቆን –ቀስቶ ወተረ

$
0
0

daniel-kibret-300x207ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በሰባኪነት የታወቀ እንደ ሆነ ይነገርለታል ። በአንድ ወቅት እዚህ አሜሪካ ሳሉ የአሁኑ የአዲስ አበባው መንግሥት ሹመኛ የሆኑ አባ ማርቆስ ፥ ያገለግሉበት ከነበረው ቤተ ክርስቲያን የነበሩ ወጣት ክርስቲያኖች ፥ ዲያቆን ዳንኤል መጥቶ ማስተማር አለበት እያሉ ያስቸግሯቸውና ይጋበዛል ። ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ለማስተማር መዘጋጀቱን እንጂ ከዚያ ያለፈ ነገር አለ ብሎ አላሰበም ። ካህኑ በል ነገ የምታስተምረው አንተ ስለ ሆነክ ፥ ቀደም ብለህ መጥተህ በዲቁና ቀድሰህ ታስተምራለህ ይሉታል ። ዳኒ ትንሽ ያቅማማል ። አሁንም ይጫኑታል አይ ቅዳሴ እንኳን አልችልም ይላል ። በዚህ ጊዜ “አፈረች ዲያቆን” ታዲያ የዲቁና ቅዳሴ ሳትችል በየት አልፈህ አስተማሪ ሆንክ በማለት “አፈረች ዲያቆን” ብለው ተርተውበታል ። -–[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ—–

The post አፈረች ዲያቆን – ቀስቶ ወተረ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live