Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ነፃነት በቬሎ –በሠረገላ¡ ይቻል ይሆን? -ከሥርጉተ ሥላሴ

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 30.03.2014 / ሲዊዘርላንድ ዙሪክ

በዬጊዜው እያሰገረ የሚነሳ ግርሻ መልስ ይሰጥበት ዘንድ ከህሊናዬ ጋር ተስማማሁ።

ከሥርጉተ ሥላሴ 02.023.2014 (ሲዊዘርላንድ - ዙሪክ)

ከሥርጉተ ሥላሴ 02.023.2014 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

ትናንት ዕለተ  ሰኞ 02.03.2015 ከፀሐፊ አቶ ክንፉ አሰፋ የተጻፈ ጹሑፍ አነበብኩኝ። ሚዛን የሚዳፋ ስለነበር ማንበብ፣ ማድመጥ ብቻ ሳይሆን አስቀመጥኩት። በመንፈሴ ባንክ። ከዚህ ባሻገር ከቀደሙት ሶስት ጹሑፎች በመነሳት የሚሰማኝን ከመግለፄ በፊት ከመጨረሻውና ከአራተኛው ሃሳብ ከጸሐፊ አቶ ክንፉ አሰፋ ልነሳ ወደድኩኝ። የሌሎችን ጸሐፍት በጥቅሉ እሄድበታለሁ። የማከብረውት ፀሐፊ አቶ ክንፉ ለመሆኑ ሱዳን ለኢትዮጵያ ምኗ ነበረች? አጋጣሚ ጠብቃ ለማጥቃት የማትዘናጋ የጉሮሮ አጥንት ነበረች። ነገር ግን በዘመነ ደርግ ሥርዓቱን የተጠላ ሁሉ የመሸገው ሱዳን ነበር። ሱዳንም የተፈለገውን ሁሉ ከአቅሟ በላይ አድርጋ ከብክባ ጎጆ አውጥታ አሁን ያለውን ምስቅልቅል ሁኔታ ሸልማናለች።

ወደ እለታዊ ኑሮ ስንመለስ ቀለል ያሉ ምሳሌዎችን ላንሳለዎት እንሆ ወደድኩኝ። በአንድ የህክምና ማዕከል ውስጥ መሳሪያዎች የጋራ ግን የተለያዩ ሃኪሞች በተለያዩ ህመሞች ልዩ ስልጠና ያደረጉ ይኖራሉ። አንድ በሽተኛ ወደ የወል የህክምና ማዕከሉ ሲሄድ ቀጥ ብሎ የሚሄደው ለህመሙ ቀጠሮ ወደ ሰጠው ሃኪም ይሆናል። ለበሽታው ኃላፊነት ከሚወስደው ሃኪም፤ ይህ ማለት የዓይን ከሆነ – ከዓይኑ፤ የጨጓራ ከሆነ — ከጨጓራው፤ የሳንባ ከሆነ ከሳንባ፤ ለራዲዎሎጂ ብቻ ከሆነም እንዲሁ። …  ሌላም ምሳሌ ልስጥ ፈርማሲ መዳህኒት ሊገዛ ሲኬድ ፈውስ የሚሰጡ፤ የሚያስታግሱ በርካታ መዳህኒቶች በብዛት ተደርድረዋል። እርሰዎ የሚገዙት ግን ለሄዱበት ጉዳይ ትእዛዝ የተሰጠበትን ወረቀት ሰጥተው መፈወሻውን ወይንም ማስታገሻውን ተቀብለው ይመለሳሉ እንጂ ያዩትን ሁሉ መዳህኒት አይሸምቱም። … አሁንም ሌላ ተጨማሪ ላንሳ … አንድ የገብያ አዳራሽ ይሄዳሉ የዓለሙ የምርት ውጤት ሁሉ ያለበት ነው። ሱቁ ምስቅልቅል ብሎ እደሳ ላይ ሊሆን ይችላል፤ እርሰዎ የሄዱት ግን አንድ የትራስ መብራት ከሆነ ያንኑ ገዝተው ይመለሳሉ፤ ሌሎችም ጉዳዮች ካሉበዎት የሚፈልጉትን ብቻ ይገዛዛሉ እንጂ የጭነት መኪና ተከራይተው ዓይነዎት ያዬውን ሁሉ ካልገዛሁ ብለው እንደማይገለገሉ እርግጠኛ ነኝ።

በሌላ በኩል ኃያላን መንግሥታትም ለኢትዮጵያ ቅን አስበው አይደለም የምንሰደድባቸው። ቁጭ ብድግ ብለን መኖሪያ ፈቃድ ለማግኘት ወድቀን እምንነሳው …. ቀን ለማሳለፍ ነው። አበው „የሚያልፍ ዝናብ አይምታህ ይላሉ“ ከዚህ አንፃር ይዩት ያቀረቡትን ትንተና። እኛ መጠጊያ ቢስ ነን። በሀገራችን በኢትዮጵያ የተሰደድን ውጪ ሀገርም ስደተኞች። ስለዚህ  መነሻችን ሆነ መዳረሻችን  ለእኛ ችግር ከቀረበው ጉዳይ ጋር በሚያያዙት መስመሮች ብቻ ነው አትኩሮት አድርገን ቀን ለመሳለፍ ጥግ የጠዬቅነው ….. እሺ  የእኔ ክብር።  ምርጫ የለም ማለት የለማኝ ተጓዳጅ አንሁን ማለት ነው። ጹሑፎዎት „ሰው መሆንን“ የሚጠይቅ ጉልበታም ስለሆነ መንፈስን አብዝቶ ይሟገታል። ነገር ግን ዛሬ ውጪ ግቢ ነፍስ ላይ ላለ ብሄራዊነት ለነፃነት ትግሉ ጠረን የሚመቹትን፤ ከጠላትን ሴራ ጋር የማይተባበሩትን ነጥቦች ላይ ማተኮሩ የነፃነት ትግላችን አቅም ፈተና እንዳይገጥመው ብቻ ሳይሆን አቅማችንም አይሻማም። በንፋስ ምችም ዝቅ ሲል ብሮንካይት ከፍ ሲል አስማ አያጠቃውም። ልብ ያለው ሸብ። ዋጥ አድርጎ የሚቻል በሽታና መከራ አለ። ስደተኝነት የስጋት ጥገኛ ነው። ነገም እንዳነሷቸው ዓይነት የወገን ጥቃቶች ኤርትራ ላይ ሊኖሩ እንደሚችሉ ይሰቡ እባከዎትን፤ በትሃ ጠጅ /አፍለኛ/ አይመረጠም ስለምን? ሆድ ስለሚነፋ፣ አፍለኛ እንጀራም እንዲሁ፤ ስለምን? ማር – ማር ስለሚል፤ ጀርባውም የእንጀራነቱን ቀለም ስለሚነሳው ከወጥ ጋር ስሙሙ ስለማይሆን። ስለዚህ ለአፍለኛ ጠጁም ሆነ እንጀራው ቀን ይተከልላቸዋል። አረብ ሀገር ወገኖች ይተማሉ። ከሞት ሸሽተው ወደ አልታወቀ ሞት፤ ሀገር ቤት የነፃነት ትግሉ ፓርቲዎች ከገዳያቸው – ከሚያሳድዳቸው፤ ከሚያሥራቸው ጋር አብረው በተፎካካሪነት ለመስራት ይተጋሉ፤ ከማህላቸው ተጠቂ እንዳለ አውቀው ይቀጥላሉ – በትጋት። ወያኔ የበጎ ህልም ጠላት እንደሆነ ጠፍቷቸው አይደለም በመከራ ውስጥ ኩራዝን ለማግኘት አሳር እንዲረማመድባቸው ፈቀዱ፤ ስለሆነም ፍላጎትን በማፍታታ ቀንን መተርጎም ግድ ይለናል።

አሁን ከሳምንት በፊት ወደ ጨርስኩት ሃሳብ ልመለሳችሁ። ከአንድ ወንዝ የተቀዱ የሚመስሉ ቀለሞችን ዘሀበሻ ላይ በተከታታይ አነበብኩኝ። ሦስት መንትዮሽ። መልካም ነው ሃሳብን ሳያሽጉ እንዲህ እንደ ወረደ በነፃነት መልቀቅ ማለፊያ ነው። የነፃነት ትግሉ ክፍለ አካል በዚህ መንፈስ ይቀጥል ዘንድ ነው ተስፋው ሆነ ራዕዩ። ስለዚህ ወገኖቼ የሚሰማቸውን – የሚያልሙትን ሆነ ተቆርቋሪነታቸውን በሰፊው ሂደውበታል። እንዲህ ፊት ለፊት ተገናኝተን ክርክር ማደረግ ቢቻል መልካም ነበር። ሃሳብና ሃሳብ ተቧክስው ዳኛው አሸናፊው መንፈስ እንጂ የካንጋሮ መሰል ወልጋዳ ሚዛን ባልሆነ ነበር። የሆነ ሁኖ ደንበር ከገፉት ቃሎች ውጪ ያለው መንፈስ ሁሉ ቀና ናቸው ሊያድጉ – ሊዳብሩ – ሊበረታቱ ይገባሉ። በተረፈ አድማጭ መርጦ መሸመትም መከዘንም ስለሚችል ይበይንበት እንላለን እኛ ከዚህ ከኮሽ አይሏ ቤተ – ጸጥታ ተሲዊዝዬ ያለነው ሥርጉተና ብዕሯ ….

ሦስትዮሾችን ደጋግሜ አነበብኩ። አዳመጥኳቸውም። የስሜቱ ድልድይ ያው የወንዝ ልጅነትን ያነባል። ነፃነት በቬሎ -በሠረገላ መንገዱን ጨርቅ ያድርግ ቢባል ከቶ እርግማን ይሆንብኝ ወይንስ ምርቃት። …. አይታወቅም። ለነገሩ ይህ የነፃነት ፍላጎት የሚባለው ሸንኮፉ ወይንስ ዘሩ ይሆን ያለው? …. ችግርን ውጦ፣ ችግርን አርግዞ፣ ችግርን ለመገላገል …. መርዝም ይበላል። አሁን እኔ እህታችሁ አልኳችሁ ዓይኔንም ሆነ ጥርሴን ያመኛል። እንዲያው ቅንጭብ አድርጌ ነው የምነገራችሁ። የጤናው ነገር የዚያን ያህል ነው። እናላችሁ የምር ከዓይኔ ስቃይ የጥርሴ ይሻለኛል። የጥርስን በሽታ የምታውቁት ታውቁታላችሁ የስቃዩን ምጥ፤ ግን ከዚህኛው የስቃይ ምጥ የዓይኑ ይብስብኝ እና ምነው ዓይኔን ትቶ ለዛሬም ሆነ ለሁልጊዜ ጥርሴ ቢሆን እላለሁ። በሽታ ምኑ ይመረጣል?! ዓይንም ጥርስም የዓይን አካል ናቸው። ግን ከበዛው ስቃይ ለአመልም ቢሆን የፋታ ጭላንጭል የሚታይበት ይሻላል በማለት  እንጂ የጥርሱም አይጣል አያድርስ ነው። ዓይንስ አንዱ ብቻ ነው። ጥርስ ግን 32 ክ/ጦር ያለው መሆኑ ብቻ ሳይሆን አዝማቹ ሻለቃ ምላስ አለ፤ ምስለኔው ትናጋም፤ ቁልቁለት ላይ ያለው የክ/ጦ ማዘዣ ጣቢያው ኮ/ ጉሮሮም አለ። ህም መግቢያውስ የደጀ ሰላሙ ሁለቱ ባሻዎች ባለ እርግብ ክንፎችም ቀኝና ግራዎችም እነ ከንፈርም …. ወዮ! … ድድ ድድ ድድ እነሱስ ሁሉም አብረው ነው የሚሾቁት። እነ አንጀትም ይንጫጫሉ ራህብ ፈጀን እያሉ ….  ይህም ሆኖ የጥርሱን ስቃይ እምርጣለሁ። ከልቤና ከእውነቴ ነው የምነግራችሁ። በተለይ ክረምት ዋናውን በር ክርችም አድርጌ ንፋስ እንዳይገባ አድርጌ መሄድ እችላለሁ፤ ዓይንን ግን እንዴት … ሞት ላይ ሆኖ ሠርግ፤ ጉሮሮ ማርጠቢያ በሌለበት ኬክ፤ ከፈን የሌለው ቬሎ፤ አህያ የሌለው ማርቸዲዝ ለሠርጉ ይመኛል። መመኘት መልካም ሆኖ ሳለ ለተስፋ ስንጥር ፈጥሮ እርሃብን ማባበስ ግን … አይገባም። ምን እንዲሆን እንደሚፈለግ አይገባኝም – ፈጽሞ። ይህቺ ቃሏ ጣፋጯ ነፃነት ስትደገም – ስትሰለስ ….“ እንዴት ብዬ ልምጣ ከፈለጋችሁኝ?“ ስትል ደግሞ በሠረጋላና በቬሎ ይሆናል መልሱ። ዘመናይነት በጣም የበዛ። ቅልጣን ነገር ….  ልቅቅ ያለ ይባል ይሆን?  ከጦርነት ምን ይተረፋል? አመድ ብቻ። ግን አማራጭ ከጠፋ ምን ይደረግ? ሞት የናፈቀው ሞትን የሠርጉ ያህል በፆም በፀሎት የሚለምን ፍጡር ምድር ላይ አለን። ጭብጡ። መንገድ ሲጣፋ፤ ጉም ተስፋን ሲያለብስ፤ እረመጡ ከሥጋ አልፎ መንፈስን ሲቀቅል …. ምስጥ ዘርን በዘረኝነት ትእቢት አመድ ሲያደርግ … ዝም ይሻላልን? እንዲያው ዝምም – ህም። ከቶ አንድነት ብሄራዊ ራዕይ ጠቀም ፓርቲ ጠበንጃ ቢያነሳ ሊፈረድበት ነውን?!

ናጋሳኪና ሄሮሽማ /ጃፓን/ –  አሜሪካ፤ ጀርመንና እንግሊዝ፤ እስራኤልና መላ ዓለም ምን እና ምን? ጃፓንና ቻይናስ። ሌላው ይቅርና ምስራቅ ጀርምንና ምዕራብ ጀርመን ምንና ምን ነበሩ? ወዳጅና ወዳጅ እንዳትሉኝ። የቅኝ ግዛት መስፋፋት – እና ተገዢዎችስ? አንደኛውም ሆነ የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ሂደቱና ውጤቱ፤ የሶሻሊዝማና የካፒታሊዝም ዘመን ውጊያ ምንድን ናቸው? ኔቶና ዋርሶስ? ….. ዓለም ምህረትን የተማረባቸው፤ ዓለም ለቀጣይ ትውልዱ ቅራኔን ችግሮችን በፈርጁ ፈቶ ሰላምን ለማውረድ ሀሁ የቆጠረባቸው የፊደል ገበታዎች ናቸው። የዓለም አንዳዊነት ሃይማኖቶች ነበሩ ዘመናተ – ስቃዮች ማለትም ልቻል። በዬትኛውም ሁኔታ በደል፤ በደሉን ተከትሎ የሚመጡ ሰቆቃዎች፤ ግፎች ቢደመሩ 8ኛ 9ኛ 10ኛ ሌላ አህጉር ሊፈጥሩ የሚችሉ ዬህዝብ ዬሥልጣኔ ልዩ ማህለቅ በሆኑ ነበር፤ ግን ሆነን? አልሆነም። ዘመን የሚሰራቸው ወይንም የሚገነባቸው ታሪኮች መልካሞችንም ሆነ መልካም ያልሆኑትንም ነው። መልካም ያልሆኑት መልካም ካልሆኑበት ውስጠ – መሠረት ተነሰተው አስተምረው ፍቅርን ማምረት ካልቻሉ ከታሪክ ማህደር መሰረዝ አለባቸው እላለሁ – እኔው። እኔ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ሥልጣን ቢኖረኝ እማደርገው ይሄን ነበር። እራሱ አሁን ያለው የዓለም ክረት ፍጥጫ ከዘመኑ ጋር ቢታይ ባይ ነኝ። ስለምን? ነገ ዓለም ምደረበዳ የመሆን ዕድሏ ሰፊ ነውና …. ስጋት የዓለም ዜጎች የወል መለያ በሽታ …. መሆኑ በአሁኑ አያያዝ አይቀሬ መሆኑ ብቻ ሳይሆን አካሚውም ተጠቂ ስለሚሆን ፈዋሽ አልባ ትሆናለች – ዓለም።

ከአህጉራችን ተነስተን ወደ አፍሪካ ቀንድ ከዛም ወደ መካከለኛው ምስራቅ አፍሪካ ስንሄድ እኛ ተግተን ልንሰራበት የሚገባው መሰረታዊ ጉዳይ ለአፍሪካ ቀንድ ሆነ ለመካከለኛው ምስራቅ የሰላማ ቀጠና ከማድረጉ ላይ ነው። ዕምነት ካለን የምንመራበት ቁራን ሆነ ወንጌል የተሠራልን ሰውን ሰው አውሬ  እንዲሆንበት ሳይሆን፤ ሰው ለሰው የተፈጠረ የመኖር ሚስጢሩ በመሆኑ የሚጣፍጠውም የሚያመረውን ተጋርቶ ቀጣይ ትውልድን በሰላም መገንባት ከመቻሉ ላይ ነው። አህጉራችን ደሃ ናት። አህጉራችን በድህነት ብቻ ሳይሆን በሥልጣኔ የተጎተተች ናት። የጦርነትም ቀጠና ናት። የአንባገነኖችም መፈንጫ ናት። ይህም ብቻ አይደለም ጥቁር በመሆናችን የወንጀሎች ሁሉ መፈጠሪያ ተደርገንም እንታያለን። ዲሞክራሲ ለእኛ የእንጀራ እናት ተድርጎ ስለሚወሰድ እንደ እንሰሳ ኑረን እንደ እንሰሳ እንድናልፍ ትውልድ ለትውልድ ውርርሱ – ሰቆቃ – ኋለቀርነት – ራህብ – በሽታ – መሃይመነት – ጦርነት -ችግር እንዲሆን ነው፤ እኛ የዛሬ ትውልድ ባለ ዕጣ ፈንታዎች ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ሰው በመሆናችን ብቻ ቢያንስ ለአህጉራችን ለእማማ አፍሪካ አንድ ደረጃ ከፍ ማለት ተግተን መሥራት ይኖርብናል። እንደ ፍቅር ምን ይመቻል? ፍቅር የመኖር ስበት የግንኙነት ሚዛን ጠባቂ ነው። አፍሪካ እንደ አውስትራልያ አህጉርና ሀገር ብትሆን አታልሙም። እኔ ግን ህልሜ ይህ ነው። እንኳስ የአንድ እናት ጡቶች ኤርትራና ኢትዮጵያ። የበደለ የከፋ የሚማረው እኛ ለማስተማር ስንዘጋጅ ብቻ ነው። ጸጸት የሚወለደው ከምህረት ነው። ከምህረት ደግሞ ትውልድ …. ፍቅር ሰላም ተስፋ ….. የልብ በር ምህረት ነው። ዋናው።

እኛ ባለንበት ትውልድ ከፍ ሳንል ሁልጊዜ ጎሮ ለጓሮ እንዳማን፤ እንደ ሰነጠርን፣ እንደ ተረተርን ቂም ጠንስሰን ቂም ደፍድፍን ቂም ጠምቀን ቂም ዘክረን መኖር ከመቃብር በታች እንጦርጦስ ነው ለእኔ። ሥልጣኔው የፈጠረልን መንገድ ድልድዩ ከቂም በቀል የጸዳ ይቅር ለእግዚአብሄር የሚያስባብል፤ የተጎዳ ተጠግኖ፤ አይዞህ ተብሎ ተደግፎ ነገን ማንጋት ነው። አዛውንትነት፣ ተመክሮ፣ ዕድሜ የትምህርት ደረጃ፣ መሰልጠን ሁሉ ለነፃነት መባተል ቀርቶባቸው ለነገር ድውለት ከሆነ ድካሙ ሁሉ የተቃጠለ ዘመን ይሆናል። ህግ ያጠናውም፤ ፍልስፍና ያጠናውም፤ ስፔስ ኢንጂነሪ ያጠናውም፤ ህክምና ያጠናውም መሬት ላይ ከእኔ ከማህይሟ ጋር እኩል ተሰልፎ አለማወቅን – ጭቅጭቅና ጠብን ፈልፋይ ነገርን ሲያድስ ሲሸነቁር ከዋለና ካደረ ላጠፋው የእውቀት ጊዜ ሆነ ላፈሰሰው መዋለ ንዋይ እንደ ተቃጠለ አውቆ ዘመንን ይቅርታ መጠዬቅ ያለበት ይመስለኛል።  ማደግ በፂም ወይንም በዲግሪ አይደለም። መሸበትም በጸጉር አይደለም። ማደግ ዘመኑ ለፈቀደው ጥያቄ እራስን አመቻችቶ ተዘጋጅቶ መጠበቅና ከራስ መጀመር ነው። አውንታዊነት በራሱ ሰላምና ጤና ነው። አሉታ ደግሞ በሽታ እና ጦርነት ነው። በግልም ኑሮም ቢሆን ጸጋቸው እንደ ተፈጥሯቸው ይሸረሽራሉ ወይንም ይገነባሉ። ግንባታው የታሪክ – የትውልድ – የዘመን – የትውፊት ተጠያቂነት ይመልሳል። ፍርሻው ደግሞ ሀገርም አህጉርንም ያሳጣል። ይህ ደግሞ እንደ ቀለማችን „ባሪያዎች ኒግሮዎች እንሰሶች“ እንደሚሉን ሆነን እንድንገኝ እኛ ፈቅደናል ማለት ነው። ፈርመናል ማለትም ነው።

ትብትብ ሌላውን ጠልፎ የሚጥል ይመስላል፤ መጀመሪያ የሚጥለው ግን እራሱን ነው። እኛ የትውልዱ አባል ስለሆን አልፈንበታል። እናውቀዋለን። ከቤተሰቡ በአንድም በሌላም መንገድ ያልሞተበት፤ ያልተሰደደበት፤ ያለተንገላታበት ሰው በነቂስ አይገኝም። የኛ የትግል ሚስጢር ለዲሞክራሲ ብቻ ሳይሆን ቀዳሚው ከወያኔ ሃርነት ትግራይ ባርነት ነፃ መሆን ነው። ከነፃነት በኋላ ደግሞ ለታላቁ ዴሞክራሲ። ግዴታችን በምድራችን በኢትዮጵያ በአህጉራችን በአፍሪካ ይህ ወጣት ትውልድ ያለበላውን ዕዳ የሚከፍልበትን መጋረጃ ቀዶ እንደ ተፈጥሯቸው ወጣቶች በዘመናቸው፤ ዘመናቸው የፈቀደላቸውን አድርገው ዘመኑንም በፍቅር መምራት ይችሉ ዘንድ ካለስጋት ይኖሩ ዘንድ ማሰናዳት ነበር። ቢያድለን። ለወጣቱ ትውልድ መከራ ሳይሆን፣ ስቃይ ሰይሆን የተረጋጋ ኑሯቸውን የመገንባት ድርብርብ ሃላፊንት አለብን – የቀደምነው። አንድ ትውልድ አለቀ። አንድ ትውልድ እንደ ተናከሰና እንደ ባከነ ወደመ። አሁን ደግሞ በዚህ ይቀጥል ነውን? …. በቀል በበቀል ይተጫጨድ ነውን? የኔዎቹ ክብረቶቼ ከልብ ሁናችሁ ብታስቡት የተሰደዱ ወገኖቻችን ትንፋሻቸው የጠብታ ጥግ ያገኙት ምን የዬት ሀገር ዜጋ ነን ብለው ኬዝ ቢሰጡ እንደሆነ ልባችሁ ያውቀዋል። ኢትዮጵውያን እንኳንስ መኖሪያ ፈቃድ ያላገኙት ያለን እንኳን በስውሩ የወያኔ ሴራ ተባባሪ ሃይላት መቀመጫ አለገኘነም። የሌላ ሀገር ዜግነትን መወሰድም አቅሙ ምን ያህል እንደሆነ አይታችሁታል። ….. ትንሽ እንደ እድሜያችን ሚዛን ይኑረን ….. ፍርድና ዳኝነት ደግሞ ሥልጣኑ የመዳህኒተአለም እንጂ የሰው አይደለም።

በሌላ በኩል የጋዜጠኛ ህጉ ደንበር አልተሰራለትም። አቅም ከኖረ የትም ቦታ የቀለም፤ የድንበር፤ የሃይማኖት ቦታ ሳይገድበው ዕውነትን ፈልጎ ለማግኘት የመረጃ ምንጭ ተግባሩን የመወጣት ሃላፊንት አለበት – ጋዜጠኛው። አይደለም ኤርትራ መሄድ ኤርትራ ላይ ኢሳት፤ ኢራቅ፤ እስራኤል፤ ደቡብ ኮርያ፤ አርንጀንቲና፤ ካሜሩን፤ ማዳጋስካር፤ ሜክሲኮ የኮርስፓንዳንስ ሠራተኛ ቢኖር ነውሩ ምኑ ላይ ነው? እንደገናም የፖለቲካ ጋዜጠኛ እንደ እስፖርት ወይንም እንደ ሞድ ወይንም እንደ ማህበራዊ ወይንም እንደ ሳይንስ  ጋዜጠኛ ሊሆን አይችልም። የሙያው ሥነ ምግባር ሆነ ተፈጥሮው አይፈቅድም። እንዲያውም የፖለቲካ ጋዜጠኞች የደህንነት፤ የህግ፤ የሰብዕዊ መብት አያያዝ ተጨማሪ ሥልጠና ቢሰጣቸው የሙያቸውን ሥነ ምግብር ምን ያደርገዋል? ይመጥነዋል። ማለት ልቅ ሳይሆን በልክ ጊዜን ያደመጠ፤ ወቅትንም ያጠመደ፤ ተስፋን የከበከበ፤ ጥንቃቄ የተካነው ግን ግነት ያልዘፈነበት ያደርገዋል። ወሳኝ ጥያቂዎች ዘመኑን የሚንዱ ከሆኑ፤ ለዘመኑ ትርፋማ ካልሆኑ መዘለል አለባቸው። ይህ ስልጠና ሲወሰድም አበክረው መምህራኑ የሚገልጹት ነው። በሌላ በኩል ሰው መብት አለው የሚፈልገውን የመወሰድ ወይንም የመተው። ማን በግድ ተሸከም ብሎ ያስገድደዋል። ለዛውም በብዙ ሁኔታ በህይወት ተቆርጦ ለተሄደበት ጉዞ ሃጢያቱ የኪሎ ማንጃሮ ተራራ ያህል መሆን። ቁስለት! …. ተጠልፈው ለበለሃሰብ ተሰጥተው ቢሆን ደግሞ ውዳሴው ድርሳን ይጻፍላቸው ነበር። ፎቶው ዝክረ ማህደር ይሆን በነበረ …. ተዛነፍ ፍላጎት – ነፃነትን የማለም አቅሙን እዩት – ቀጭጮ ታቱ ሲል …. ይቅር ይበለን አባቴ።

አንድ ጥግ ላጣ ተማላ ዜጋ፤ መሬት ላጣ ሥጋና ደም፤ ውሃ ጠምቶት ሲጠወልግ ቀና አድርጎ በአፉ ምራቅ ያረጠበ ማንም – ምንም ይሁን ለእኔ ጻድቅ ነው። ለነፃነት ካለ ደሞዝ በነፃ ወጣትነቴን፣ አዛውንት ወላጆቼን፣ ናፍቆቴን ኢትዮጵያን ትቼ ወይንም የኑሮ ጣዕሜን ሁሉ እሰጣለሁ ብሎ ለቆረጠ ጀግና ትንፋሽ ቢያጥረው፤ ቢቆስል፤ ተስፋ ቢያጣ ሜዳ ላይ በአፉ አፍንጫውን ምጎ ትንፋሽ የሚለግሰው ለእኔ የነፃነት ረሃቤ መልካሜ ነው። የጨነቀው፤ የቸገረው፤ ማጣፊያው ያጠረበት፤ መብራት የሌለው፤ የሀገር – የቦታ – የምቾት ሆነ የሰው ምርጫ ጥያቄው አይደለም። ለዛውም የሚያማርጡበት በሌለበት ሁኔታ። አንድ ነጭ ከመንገድ አግኝታችሁ አንዲት ከሚያወቃት ኢትዮጵያዊ ቋንቋ ያናግራችሁ። ምን የሰማችኋል? የሀገር ናፍቆት – ሰቅሰቅ አድርጎ ከአብራክና ከማህፀን የሚያስለቅስ ሰቀቀን ያለባችሁ ወገኖቼ። ዕውን በእውኔ ነውን? የሀገሬ ጠረን በዬት መጣ ብላችሁ ክፍትፍት ባደረገው፤ የስደት ንፋስ ብጥርቅርቅ ባደረገው መንፈሳችሁ ውስጥ አዲስ ሰናይ አይሰማችሁንም?! እኔ እውነቱን ብናገር„ በርቀት የቡናውን ጭስ ሸተትን፤ በርቀትም ሁመራ ማርያምንም አዬን። ሰቲት ሁመራ ሀገራችን ግን እንድንረግጣት ያልተፈቀደችልን“ ጋዜጠኛ መሳይ መኮነን …. እኔ አለቀስኩኝ። እናቴ ተስላ ዬልቧን ያደረሰችላት ሁመራ ማርያም፤ ጀግና አርበኛ አባ ሻንቆ መለሰ ኃይሉ ከአርበኝነት መልስ ዬኢትዮጵያን ሰንድቅ ዓላማ አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን ከፍ አድርጎ በማህል አናቷ ሰቲት ሁመራ ላይ ያውለበለበባት፤ የአባቶቼ የቅድመ አያቶቼ አጽም እርስት፤ እኔም ለአቅመ ህይዋን ስደርስ ሄጄ ወገኖቼን ያደረጀሁባት ቦታ የትናንት የጎንደር ክ/ሀገር የዛሬ የወራሪውና የዘራፊው ዬወያኔ ሃርነት ትግራይ ዘራዊ አፓርታይድ አገዛዝ መፍንጫ ሰቲት ሁመራ – ተከዜ፣ አልፎም አብደራፊ አንዲያም ሲል ኡምናሃጅር ሽው – ውል – ንፍቅ አለኝ፤ ተባረክልኝ አባትዬ በመንፈሰም ቢሆን ለናፍቆቴ ወጌሻ ስለሆንከው …. ኑርልኝ። እና ሠራዊቶቻችን የእኛዎቹ የሀገራቸውን ጠረን በቅርብ እርቀት፣ የቋንቋቸውን ምት ላሂ በውስጡ፤ የባህላቸውን ጸዳል በምልዕት፤ የሃይማኖታቸውን ሥርዓት በተደሞ እንደ እራሳቸው በሚዳስሱበት ቦታ መገኘት አንዱ የመንፈስ ማስያዥ ህክምና ብቻ ሳይሆን መንገድ ጠራጊ እንዲሁም ጠባቂ፤ ከብካቢና አበረታች …. አፅናኝ የማሸነፊያ ኃይል ሰጪ አይደለምን?! ውትድርና እኮ ፈቅዶ ኑሮን ሳይሆን ሞትን በፈለገው ፎርምና ይዘት መቀበል፤ መከራን በድምጸ ሙሉ ውሳኔ በራስ ላይ መጫን ነው። ለዛውም በነፃ መሃያ አልቦሽ። …. እህት – እናት – ወገን – አበልጅ – ትዳር – ልጅ – ጎረቤት በቅርብ የለም። ግን ጣዕሙ አንድ የሆነ፤ ዘመን የለዬው መንትዮሾነት በፈቃደ እግዚአብሄር ሥነ ጥበብ እንዲህ ሲኮን አያጓጓም? ይህ እኮ የሰው  ሥራ አይደለም።

እኔም የእናት አባቴን ልጅ ወንድሜን ሃይልዬን የአጎቶቼ ልጆች ከሁሉም በላይ አብሮ አደጌ የትግል ጓዴ እንግዳወርቅ ተክሌ እንደ ወጣ ቀርቶብኛል። ይግደሉት – ይስቀሉት  – በቁም ከነህይወቱ ይቅበሩት አይተወቅም። እንግዳ ዋሾ ሜዳ፤ አንገረብ መስክ ኮኮች ወንዝ አብሮኝ የቧረቀ አብሮ አደጌ በኋላም ጓዴ ነበር። ዬእንግዳ ቤተሰቦቹ ትግረኛ ተናጋሪ ሲሆኑ ዬዬትኛው ስለመሆኑ አናውቀውም። እድገታችን ጎንደር ኢትዮጵያዊነት ብቻ ስለሆነ። እንጃ ለእኔ ልዩዬ ነበር። ከካኪ አቅም እንኳን የሥራ ልብስ አስቦ ገዝቶ የሚልክልኝ የልቤ አንጎል ነበር። ሌላው ባህርዳር ላይ በአድዋ ድል ዕለት የተወለደው— የባህርዳሩ አድዋስ …. ወፌ እያለ የሚያቀብጠኝስ። እዛው ነበር የቀረው። አድዋ ከህልፈቱ ጀምሮ ቢሮዬን እስከለቀቁበት ድረስ ፎቶው ፊት ለፊቴ ነበር፤ ከቤተሰቦቹም አንድም ቀን ሳልለይ ነበር …. የተለያዬነው። ስለምን? አንቱው ሙሁር እረሱን ለእናቱ የገበረ በላይ ነበርና። እልፍ ጀግኖች ዘመን ከቶ ሊተካቸው የማይችሉ ሳተናዎች …. አጥተናል፤ ይህ ብቻም ሳይሆን ሰማዕትነታቸው ዝክረ ቀብር ተበይኖበታል። አሁን ደግሞ ብሄራዊ ማንነት በተዳጠበት ዘመን የከፋ ችግር ወቅት ላይ ነን። ስለሆነም ችግርን ደፍሮ፣ ችግር ለመቀበል ወስኖ፣ በችግር ምሽግ ለብሰው መፍትሄ ለማፍለቅ፤ በችግር ድቅድቅ ብርሃን ለማዬት በምህረት ጎዳና መጓዝ ምኑ ነው ክፋቱ? የዘመንና እሰረኛውን መንፈሳዊ አኃታዊነት ችለን ይፍታህ ብለን የቅዱስ ሐዋርያውን ጳውሎስ ምግባር ብንወስድ እንጎዳ …. ይሆን?!

ለጥፋቱ ሁሉ የዘመኑ ታዳሚዎች ነንና ሁላችንም ከተጠያቂንት አንድንም። የበርሊን ግንብ ፈርሶ አንድ ያደረገ አምላክ ቢያንስ በገጽ ፍቅርን አቅንተን ፍቅርን ብንሸምት ምን ክፋት አለው? ጥላቻ እኮ ነው ሰላምን የሚያሳጣው – አሳማው። ፍቅር የሰላም ሸላሚ ነው። ሌላው እነዛ ቀንበጦች እነዛ ማገዶዎች ስለ እውነት የመሰከሩ፤ የማንዴላን ዓላማ የተከተሉ፤ የሃይማኖት ነፃነትን የጠዬቁ፤ የሰው ልጆችን መብት በሰላም እንጂ በጦር ሜዳ በሚገኝ ትርፍ መወራረድ የለበትም ጦርነት ከእንግዲህ በቃ ብለው ነጭ እርግብን ያፈኩ፤ ሰላምን በሰላም ብለው የተሟገቱ …. ሁሉንም ሞክረው ግን ቤታቸው በበላያቸው ላይ የፈረሰው የሃቅ ማህደር አገልግል ሲፈታ ምን ይለን ይሆን? „አንድነት“ ሥሙ እንኳን በሽታ ሆኖት የወያኔ ሃርነት ትግራይ ይሄው …. ያላችሁበት ሃቅ ነው። …. ሌላው የገረመኝ ደግሞ ለማመሳከሪያነት የቀረበችው ክብርት ዳኛ ብርትኩን ሜዴቅሳ መሆኗ ነው። ዓለም አቀፍ ዕውቅናን ያጎናጸፋት መነሻ ቤቷ ቀስተ ዳመና ፓርቲ ነው። ድልድዮዋ ድግሞ ቅንጅት ሲሆን የልቅናዋ እርገቷ አንድነት ነው። ከእውነት ጋር ቡጢ መግጠም ትርፉ ምንም ይመስለኛል፤ የሚቻል ከሆነ አሁንም እኮ መሞከር ይቻል ይመስለኛል። የወንበዴው የወያኔ እግር ብረቱም፤ ዱላውም፤ ስጋቱም፤ መደፈሩም መታሰሩም በተጠንቀቅ ይጠብቃሉ – አሉ። በትጥቅ ትግሉም ቢሆን ኬኒያ፣ ጁቡቲ፣ ሱማሊያ፣ ሱዳን ክፍት ናቸው የሚችል መሞከር የአባት ነው። …… በስተቀር እዬጎረጎሩ – እዬቦረቦሩ የነፃነት ትግሉን አቅም መብላት ወይንም መንፈስን መስረቅ ጥቅሙ ለወያኔ እንጂ የቅንጣት ታክል የነፃነት ትግሉን አይጠቅምም – ወገኖቼ። ለተስፋችን ደመኝነትም ነው። የወያኔ ጀሌዎችና እና እኛ እኩል በአንድ መስመር ከሚያስገቡን ሃዲዶችና ባቡሮች እራስን ማግለል ብልህነት ይመስለኛል –  ቢያንስ ዝም። እኔ በጣም እርግጠኛ ነኝ ሰላማዊ ትግል እያሉ አንድነትን የደገፉ መስለው ግን ጉዳዩን ሲያራግቡ፣ ሲያሟሟቁ – ሲያጋግሉ የነበሩ አካላችን ከፈረሰበት ዕለት ጀምሮ ድራሽ አልባ እንደሚሆኑ ነው የማስበው። ስለምን? ድሮም የእኛ አልነበሩምና። እውነተኛው ቁም ነገር አንድነትንም ወደውት አልነበረም። መሸጎጫ እንጂ። አንድነት ለእኛ ለኢትዮጵያ ሴቶች ለትውልዱ – ትውልዳዊ ድርሻውን የተወጣ የመጀመሪያዋን ሴት የብሄራዊ ፓርቲ መሪ ክብርት ዳኛ ብርቱካን ሜዴቅሳን በአብላጫ ድምጽ የመረጠ ሆኖ የተገኘ የእኩልነት ማርዳችን – ጌጣችን ነበር።  በዐለም ዕውቅና ክብር ያላት ጋዜጠኛንም የፈጠረ። ተወዳጅ ተፈቃሪ መሪዎችን ያስገኘ። ግን ቀጠለን? አስቀጠሉትን? —– ይህን እንቆቅልሽ ከሌላ ጋር ሳይሆን ሁለት ሃሳቦችን ፊት ለፊት አቅርቦ ተጠዬቅ መቀመጥ ያለብን ይመስለኛል። ከሊቅ እስከ ደቂቅ። …. ስድቡም መቆም አለበት። ለዚህ ያልሆነ ሽበት – ጋዳ ነው ገደለ – ነገር። እንደ ዕድሜ፣ እንደ የዕውቀት ደረጃ እኛን መሃይሞችን በመሆን መብለጥ ያለባቸው ይመስለኛል … በፆም ግድፍት የሚያምራቸው ቀደምቶቹ – ደሞቼ።

ሌላው የገረመኝ ነገር። ለኤርትራ ሀገራዊነት ዕውቅና ተሰጠ ብለው የሚተቹ ወገኖች፤ ሰሞኑን የተከበሩ ፕሮፌስር  ተስፋ ጽዮን መድህኔ „“ ይሄውና ኤርትራ ሞተች ትግል ለሀገር ትንሳዔ“  ሲሉ አንድ ጹሑፍ አስነብበውናል። እርእሱ እራሱ „ሀገር“ ሌላ ቦታ ሳይኬድ ዕውቅና ነው። ገራሚው ነገር ኤርትራን እንደ ሀገር ተቀበለ ግንቦት 7 ብለው ናዳውን የሚለቁት ናቸው ፕ/ ተስፋ ጽዮንን ሲያደንቁ የማዳምጠው። እኔ ፕ/ በአካል አውቃቸዋለሁ። መቼም ሥርጉተ ቅመም ናት። 13 የምንቅናቅ /ንቅናቄ/ አንድ የግል ታጋይ በሦስት ቋንቋዎች /በትግረኛ – በአረብኛ – በእንግሊዘኛ/ በተዘጋጀው የጀብሃ መስራች አዛውንታት በተገኙበት ከመላ የዓለም ሀገሮች ብቻ ሳይሆን ከሁሉም አህጉራት የተሰበሰቡ የጀበሃ ደጋፊዎች፤ የሻብያ ተቃዋሚዎችን ጉባኤ በድንቅነት እንዲሳካ ካደረጉት ውስጥ አናቱ ናቸው – ፕሮፌሰሩ። የብቃታቸውንም ጥልቅነት በጣም ከውስጣቸው ነበር የተመለከትኩት። የሰከኑም ናቸው። ኤርትራ አለኝ ልትላቸው የምትችል ብቸኛ ሃብትም ናቸው። የእኔ ጉዳይ በእሳቸው አቅም – የተፍጥሮ ጸጋና ክብረት አይደለም። … አንዱ የሚደቆስበት ተመሳሳይ አመክንዮ ከሌላው ላይ ሲሆን ውዳሴ መሆኑ ነው የገረመኝ። … ሳልጠቅሰው የማላልፈው ሃቅ ግን የ13 ምንቅናቅ መሪዎች በጋራ ከአንጋፋ የጀበሃ መሥራቾች ጋር ስብሰባ በተለዬ አዳራሽ ተቀምጠው ነበር። እኔ ወደ አዳራሹ ስገባ በዛ ጀርጋዳ ቁመታቸው ተነስተው በመጎናጸፊያቸው እቅፍ ያደረጉኝ እንጃ ከአባቴ በስተቀር እንዲህ የሆነልኝ ንጹህ ልብ አልገጠመኝም። አይረሳኝም። በነፃ መሬታቸው መረጃ ቢያስፈልገኝ የምንቀሳቀስበትም ይለፍ ሰጥተውኝ ነበር። በቂ አድራሻም።

ለማንኛውም ዘመናይነት፤ ቅልጣን፤ ዝነጣ፤ ቅንጦት፤ ቅብጥና ቅልጥ ፍለጋ ነፃነትን በቬሎ – በሠረገላ የመመኘት ያህል ነው ለእኔ። ከሁሉ የሚከፋው ቀውስ የጎሳና የሃይማኖት ነው። በሁለቱም የተሰቀዘች ሀገር ላይ ሆነን እንደ ሃላፊነታችን ለቀጣዩ ሀገር እሰከ ዓይን ጥርሷ የማስረከብ ብሄራዊ ሃላፊነት እያለብን ግን ….?  ….. ዛሬ ስለቀረ ነው እንጂ ኤርትራና ኢትዮጵያ ከሀ እስከ ፐ ታላቅ ብሄራዊ ጉባኤ ላይ ተከታታይ ወርክሾፕ ሆነ ፓናል ዴስከሽን የማደረግ አቅም ነበረን። የማይታዋቅ ታሪክም፤ ያልተሰለጠነበት የፖለቲካ ዘርፍም አልነበረም። ሌላው ቀርቶ በዬሶስት ወሩ ይታተም የነበረው የፓርቲዬ የኢሠፓ ልሳን አካል „መስከረም“ መጽሔት እራሱ ተቋም ነበር። ለዚህ መሰሉ ታሪካዊ ትንታኔ አዲስ አይደለንም። እንኳንስ ተጫማሪ ኮርሶች ታክለው … ግን ዛሬ ላለብን የፋመ ረመጣዊ ችግር ይጠቅማልን? ነፍሰ ጡር ወገን አስፓልት ላይ፤ ቅድስት መነኩሴ አስፓልት ላይ፤ የገዳማት አበው በገዳማቸው፤ ሼኮች በመስጊዳቸው፤ ገበሬዎች በማሳቸው፤ ወጣቶች በገደል በቤንዚን እራሳቸውን በሚገድሉበት መራራ ዘመን ላይ፤ ወገኖቻችን ስቃይን እንደ ስቅለት ዕለታዊ ትንፋሻቸው በሆነበት ሁኔታ ላይ ብርንዶ፤ ጠጅ፤ ቁርጥ ያሰኘናል ለነፃነት ትግል —- ወይንስ ድንኳን ወይንስ ዲል ያለ ድግስ በአዳራሽ? ፍ – ቱ – ት —-

ለመሆኑ „የኤርትራ ጥያቄ እስከመገንጠል የማን ቅኝት ነበር“ ሌላም ሱማሊያ ኢትዮጵያን ገዝታ ብትሆን ምን እንመስል ነበር? የባድመ ጦርነትም ጊዜ ሻብያ እንዲቀጥል ያበረታታ አቋም ነበር „በወያኔ ጉድጓድ ሄዶ መሞት አይገባም“ የሚል። ሻብያ ባይገደብ ቢቀጥል ሚኒሊክ አደባባይ ሰንደቁን ቢያውለበለብ ተጨማሪ ከ74000 ዜጎቻችን በላይ ንብረት ቢወድም ዛሬ ያለው አቅማችን ምን ይመሰል ነበር? ገለጻውን በስማ በለው አልነበረም የሰማሁት እኔ ቁጭ ብዬ ፊት ለፊት ነው  የስብሰባው ታዳሚ ሆኜ ያዳመጥኩት። ለዛች ቅጽበት መርሁ ገዳይ ነበር። ለነገሩ አድማጭም አልነበረውም። ዛሬ ደግሞ ከጠላታችን ጋር ተወገነ ተበሎ ሌላ ጨዋታ …. ለመሆኑ ይህ ሃቅ ብቻውን በመጸሐፍ አሳትሞ የህዝብን መንፈስ በሃቅ ወተት መገንባት አያስችልምን? ምን ሲገድ … ግን ለዛሬ ይጠቅማልን? ይፈይዳል? ብናኝ ዕሴት አለውን? ከብጥብጥ ከአንባጓሮ ከመካሰስ በተረፈ ለዚህ በአናቱ ወያኔ ላንጠለጠለው ኢትዮጵያዊነት መኖር ይሆናል? አቻው ነውን? ቁስል እዬቀራረፉ መግል ማዝነብ ድምሩ የወያኔ ሃርነት ትግራይ ሸኮናን ወይንም ዳልጋ ማድለብ ብቻ ነው የሚሆነው።

ስለዚህ የሚጻፋው በሉት፤ ፕሮፖዛል በሉት፤ ቃለ ምልልሱ በሉት ከላፍኩበት ህይወት ውጪ አይደለም – ለእኔ። ተዛነፉን በመሰሉና በልኩ በተሳፋ ጠርቦ ማስተካከል ይቻላል። ግን ለዛሬ ያ ሚዛን ጠበቂ ትንታኔ ጠቃሚ ነውን? ያ አቋም የወያኔ ንደት ያባብሰዋል ወይስ ይደግፋዋል – ኢትዮጵያንስ እንደ ሀገር ህዝብንም እንደ ማህበረሰብ ያድናልን? …. እእ …. ለወቅቱ የሚስማማ የአቅምን ድምጽ ማድመጥ ነው ብልህነት። የለማኝ ተጓዳጅ መሆንም አይገባም።  ውዶቼ – የኢትዮጵያን ህዝብ ብልህነት ህግነት፣ እውነትነት፣ ጥልቅነት በግልቡ አንዬው። ከእኛ በላይ ህይወቱ ዩንቭርስቲው ነውና ….. መምህራችንም ነው። እንክርዳድን – ከስንዴ፤ ፍሬን – ከገለባ የመለዬት አቅሙም አንቱ ነው። ይልቅስ እኛ ያለብን ግርድፍና ሽርክት ቁንጥንጥ ፍላጎቶች ገርተን ወይንም መልክ አስይዘን ለራህቡ እንድረስለት። ምስጋናውን ቀርቶ ቢያንስ በብልህነት ወቅቱን እናዳምጥ። በትውፊታችን የምናውቀው …. የማይቻል መከራ ለሌላው ሳይነገር እሬሳ ታቅፎ፤ ዕንባ ታምቆ፤ ብዙ ቀናት ከውርዴት ወይንም ከመጋለጥ የሚያድኑ መሰናዶዎች ይከወናሉ። ያዬነውም የሰማነውም ከቤተሰቦቻችን ትውፊቶች እነኝህን ይመስሉ …. ነበሩ። እባካችሁ ክብረቶቼ እናስተውል – ፉከራ አይደለም። ከልብ እንሁን፤ በፍላጎታችን ውስጥ መኖር ብቻ ሳይሆን የፍላጎታችን ስኬታማነት ሥነ – ህግጋትን እንመርምር ለማለት ነው። የብዕር አካላዊ እንቅስቃሴዎች የነፃነት ትግሉ ክንድን የሚያጠነክሩ እንጂ የሚያዝሉ መሆን አይኖርባቸውም – ፈጽሞ። ደግሞስ መጎረጃው መቼ ነው ይሆን የሚያቆመው?! ግንቦት 7 ከተፈጠረ ጀምሮ ይሄው ነው። ሌላ ተግባር ብንከውን ምን አለ? ሁልጊዜ በአንድ ፓርቲ ላይ ናዳ መለቅቅ … ለምን? ግራ ነገር። ማገርሸት – ማገርሸት – ግርሻው ደመ ከሴ ቢፈልግ ይሻለው በነበረ። የሆነ ሆኖ የማይጥመው አለማድመጥ – አለመተባበር – የራስን ተግባር በራስ ምርጫና መንገድ በበለጠና በቀደመ ሁኔታ መከወን … በቃ! ለነገሩ ከነፍሳቸው ያልተፈጠሩ አጀንዳቸው በራሳቸው ጊዜ ይከስማሉ …. አድራሻ አልቦሽ —- ናቸውና።

የጓጓለ ስጋቴን በተሰፋማ ዕይታ …..

  1. እንደ ድርጅት ሻብያ፤ እንደ መሪ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ መፈንቅለ መንግሥት ቢደርስባቸው፤ ፓርቲያቸው ውስጥ አንጃ ቢፈጠር፤ ወይንም በሌላ ድርጅት – ድርጅታቸው ቢጠቃ እንደ ሰውም ቢያልፉ፤ የሥርዓት ለውጥ ሊመጣ ቢችል የኛዎቹ ተጠባባቂ ቦታ ብቻ ሳይሆን በአጭር ጊዜ ሠራዊቱን ከነንብረቱ ቦታ የማስለቀቅ ሁኔታን ቀድሞ ሊታሰብበት ይገባል። ከሥር ተከታታይነት አቅም ያለው ጣምራ ሥራ ሊሠራበት ይገባል እላለሁ።
  2. ሻብያ ከወያኔ ሃርነት ጋር ቢስማማስ? መጥፎዎችን አስቦ መዳህኒት አዘጋጅቶ በተጠንቀቅ መጠበቅ ያተርፋል እንጂ አያከስርም። በዚህ ዙሪያም የኢትዮጵያ ነፃ አውጪ ሠራዊት ኤርትራን የመልቀቅ ግዴታ ቢኖርብት መሸኛኘቱ በእኩልነት ላይ ተመስርቶ በምስጋና እና በፍቅር ይሆን ዘንድ ቅድመ ድርድርም ከሻብያ ጋር ማድረግ ይገባ ይመሰለኛል።
  3. ቃለ ምልሱን እንዳደመጥኩት ጭብጡ ጎጠኝነት ለኢትዮጵያዊነት አይበጅም ነው። እሰዬው ያሰኛል። ታዲያ ይህን መንፈስ ወደ ተግባር የመቀዬር የቀረበው መስመር ያለው በፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እጅ ነው። በህግ ባያፈርሷቸውም ይህን ቀና መንፈስ በጎጥ ከተደራጁት፤ ድጋፍ በቀጥታ ከሚያገኙት አካላት መሪዎች ጋራ ቁጭ ብለው መከረው፤ ሰባራ ሰንጠራውን ደፍነው ወደ ብሄራዊነት ለማምጣት የቤት ሥራውን ሆነ ሃላፊነቱን ቢወስዱት መልካም ይመስለኛል። የመገንጠልን ሆነ በጎጥ የመደራጀትን ትርፍና ኪሳራ ከራሳቸው በላይ በህይወቱ የኖረ የለምና። „ታሪክ የለኝም“ ሲሉ አዳምጫለሁ። ምን አልባት በዚህ ዙሪያ በሚወስዱት ንጡር እርምጃ ታሪካቸውን ጸሐፊ ያገኝ ይሆናል።
  4. የጎጥ ድርጅት መንፈሶች በፍሬው ትንተና ሲኬድባቸው በኢትዮጵያዊነት ውስጥ ጎጡ ሳይሆን፤ በጎጡ ውስጥ ነው ኢትዮጵያዊነት ያለው። ይህ ማለት ኢትዮጵያዊነት ደረጃው ከጎጡ በጣም የወረደ ነው። ስለዚህ ለነገ ጠንቅ ነው። ከዚህም በላይ ከእንግዲህ በኋላ የጎጥ መንፈስ አመክንዮ ዓለም አቅፍ ዕውቅና ድጋፍ አያገኝም። የአንድነት ሃይሉ ሥነ ልቦና ድል ላይ ነው በዓለም ዐቀፍ ደረጃ። በመሆኑም መሳሪያ ካነሱት ውስጥ ለዚህ ሃሳብ ቅርቡ የነገ የተስፋ ጥንስስና ጥግ አርበኞች ግንቦት በመሆኑ በመንፈስ፣ በአካል አጠናክሮ ከጎጠኞቹ አቅም ጋር የሚመጥን የግንባታ ሂደት መኖር ያለበት ይመስለኛል። በስተቀር ለነገም ጥላሸት የሚያመነጩ፣ ተስፋን የሚፈታተኑ ሁነቶች ጎልተውና ጉልበታም ሆነው ከወጡ አንጻራዊ አደጋ ሊኖረው ይችላል። ስለዚህ በኢትዮጵያ ሰንድቅዓላማ ሥር የተሰባሰቡት ካለ ጥያቄ፤ ካለ ቅድመ ሁኔታ በወጥ ፍላጎት ሥር መሰባሰብ አለባቸው ባይ ነኝ። ለዚህ ቀዳሚው የአፋር ነፃ አውጪ ግንባር አብሪ ይሆናል ብዬ አስባለሁ። የፕሬስ + የስፖርት ጋዜጠኛው ሆዅተ ብርሃን ጌጡ „የአፋሩ ቅኔ በእኔ ቅኝት“ የረቀቀ ሚስጥሩን በቅኔ ሲዘርፈው ይህን ማለቱ ብቻ ሳይሆን ከዚህ የዘለቀም ትርጉም አለው። ኢትዮጵያን ያለ ከአሸናፊው ማንነት ጋር መወገን አለበት ነው ሚስጢሩ። በተረፈ መሆንን በመከራ ሰሞናት የተረጎመውን የቀድሞው አንጋፋው ዬአርበኞች ግንባርን አመሰግናለሁ። መመካት ባይኖርም ኮራሁባችሁ። የተከበሩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሲታሰሩ ባወጣችሁት ፈጣን መግለጫ ከሥሩ ያልኩት ነበር – ሁናችሁ አሳያችሁኝ።

ስንብት ይሁን መሰል። ወጣቱ ትውልድ በህይወት ያሉ እውነታዊ ምስክሮችን አይቶ የነፃነት ትግሉን በአቅም – በጉልበት – በመንፈስ – ሥነ ህሊናውን ሳይቀር ሸልሞ ዝንቅና ቅጥ አልቦሽ ሃሳቦችን ቀብራቸውን ማወጅ አለበት። እኔ ተማሪ እያለሁ „አትማሩ“ የሚል መርህ ነበር። „አትማሩ መርህ“ 40 ዓመት ለሥልጣን አልበቃም። 40 ዓመት ሙሉ ኢትዮጵያ ያሉ የት/ ተቋማት፤ ዩንቨርስቲዎች፣ ኮሌጆች፤ ተቋማት፤ ቢዘጉ ኢትዮጵያ ምን ትመስል ነበር? በሙያው ይተዳደሩ የነበሩት ቤተሰቦችስ አዳራቸው ምን ይሆን ነበር? የኔ ጌጦች በተለይ ወጣቶች አስቡት። ስለዚህ በሰላማዊ ትግሉም ዘርፍ ቢሆን አሸናፊውን ማንነት ይዞ ወደ ተሰለፈው መትመም ግድ ይላል። ወደ ሰማያዊ ክተት ማለት ይገባል። በተረፈ ቀደምት ሰማዕታት ጀግኖቻችን አርበኞቻችን በአትዮጵያ ምድር ጦር፤ በባህር ኃይል፤ በአዬር ኃይል ተሰልፈው ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉዕላዊነት የተሰውት ጀግኖቻችን ከንክብራቸው – አንረሳቸውም። ቀን ሲያልፍ ሁሉም ይሆንላቸዋል። የሚመረውም እያንገሸገሸው እንዲውጠው – ይገደዳል። ይህ የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ የዜግነታችን የክብር ቀን ነውና። እያያችሁት ነው የሚጸዬፉት ስልጡኑ አማርኛ ቋንቋ ግራ ቀኙን እንዴት አሳምሮ አንበርክኮ እዬገዛ እንዳለ። ኢትዮጵያዊነት ሄኖክ ኢትዮጵያ ደግሞ አላዛር ናት። እግዚአብሄር ይስጥልኝ ዘሃበሻ ማህበራዊ ድህረ ገጽ – ኑሩልኝ። ለጹሑፌ ወርቅ ታዳሚዎችም መሸቢያ ሰሞናት ተመኘሁ – ከመንፈሴ ብሌን።

ቂም በቀል ዘር አክሳይ፤ ምህረት የርትህነት ውስጠ – ሲሳይ! የሥልጣኔም ስንቅ አቀባይ።

ለእኔስ ሰው መሆኔ ብቻ ከበቂ በላይ ነው!

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ፤

ትውልዳዊ ድርሻችን በህብረትና በአንድነት እንወጣ!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ ኑሩልኝ – የኔዎቹ።

 

The post ነፃነት በቬሎ – በሠረገላ¡ ይቻል ይሆን? -ከሥርጉተ ሥላሴ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

↧

የረዳት አብራሪ ሐይለመድህን አበራ ጉዳይና የአንድ አመት ጉዞው ባጭሩ -በጴጥሮስ አሸናፊ

$
0
0

እለተ ሰኞ  ፌብሯሪ 17  ቀን 2014  ዓ/ም ማለዳ

Haile Medhin Aberaአንድ  ንብረቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነና በበረራ ቁጥር ET 702 የተመዘገበ ቦይንግ 767  የመንገደኞች ማመላለሻ አውሮፕላን በጣሊያን በኩል አድርጎ ወደ ስዊዘርላንድ የአየር ክልል ይገባል። የስዊዝ የአየር ክልል ጠባቂዎችም በጧት የመጣባቸውን  ጥቁር እንግዳ ማንህ ወዴት ነህ ማለት። የአውሮፕላኑን የበረራ ሂደት ሙሉ በሙሉ በብቸኝነት የተቆጣጠረው ረዳት አብራሪ ሃይለመድህን አበራም ቆፍጠን ብሎ አኔ ነኝ ! ማለት። አንተ ማን? ምነው ምን ፈልገህ ነው ወደ አየር ክልላችን የገባኸው?  የአየር ክልል ተቆጣጣሪዎቹ ቀጣይ ጥያቄ ነበር ። የበርካታ ወገኖቹን የብሶትና የግፍ መልዕክት ይዞ በስዊዝ  አየር ላይ የሚያንዣብበው ሃይለመድህንም  “ለጊዜው  የምፈልገው  የስዊዝ  መንግስት የፖለቲካ  ጥገኝነት እንዲሰጠኝ ፣ ለኢትዮጵያ መንግስትም  ተላልፌ እንዳልሰጥና  አውሮፕላኑን ጄኔቫ  ላይ በሰላም  ማሳረፍ ነው” የምትል ቅልብጭ ያለች ቃል ነበረች። በሁለቱም በኩል የተለያዩ መረጃዎችን ከተለዋወጡ በዃላ አውሮፕኑን ማሳረፍ እንደሚችል የተፈቀደለት ሃይሌም በተካነው ልዩ የማብረር ችሎታ ካለምንም ኮሽታ አውሮፕላኑን ጄኔቫ ክዋንትራን አየር ማረፊያ  202 መንገደኞችንና የበረራ ሠራተኞችን እንደያዘ በሰላም አሳርፎ ፤ እሱም “ያልጠረጠረ”  የምትለዋን ብሂል ቋጥሮ  ይዟት ነበርና  በመስኮት  በኩል  በገመድ  በመውረድ ለስዊዝ የደህንነትና ፖሊስ አባላት እጁን በሰላም በመስጠትና ቃሉንም  ለማስመዝገብ ወደሚመለከተው የመንግስት መስሪያ ቤት  አመራ።

ሃይለ መድህን የአውሮፕላኑን የበረራ ሃላፊነት በብቸኝነት ከተቆጣጠረ ጀምሮ ከስዊዝ ፖሊሶች ጋር በአካል አስገተገናኘበት ጊዜ ደረስ ያደረጋቸውን በሙሉ በአፅንኦት የተከታተሉ አንድ አሜሪካዊ የቀድሞ ፓይለትና አሁን ደግሞ የግል የበረራ ተቋም ባለቤትን እንዳስደመማቸው እንደገለፁለት ወዳጄ ጋዜጠኛ አበበ ገላው አጫውቶኛል።

ከዚያስ ፧ ከዚያ በኳላማ የአለም ታላላቅና ታናናሽ የመገናኛ ብዙሃን አውታሮች ዋና ዜና ሃይለመድህንና የተጠለፈው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ሆነ። የቴሌቪዥን መስኮቶች በሃይለመድን ምስሎች ተሞሉ ፣ ሬድዮኖች ደጋግመው ደጋግመው ስሙን ያነሳሉ፣ ማህበራዊ ሚዲያዎች እነ ፌስቡክና ትዊተር ስለ ሃይለመድህን በሚያወሱ ወሬዎች ኮሜንት ፣ ላይክ ፣ ሼር እና  ሪትዊት ስራ በዝቶባቸው ነበር።

በአራቱም መአዘን የሚገኙ የጦቢያ ልጆች ቀፏቸው እንደተነካባቸው ንቦች ተነሱ። ሃይለመድህን ነፃ ይሁን የሚሉ ድምፆች ማስተጋባት ጀመሩ። ” ነፃ ሃይለመድህን ” የሚል አለም አቀፍ አስተባባሪ ግብረ ሃይል ተቋቋመ ፣ ሰላማዊ ሰልፎች በመላው አለም  በከፍተኛ ድምቀት ተካሄዱ ፣ በሃይለመድን ስም  ድረ ገፅና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆች ተከፈቱ ፣ “ሀይለመድህን ብሔራዊ ጀግናችን ነው” የወቅቱ መሪ መፈክርም ሆነ።

አዎ!  ሕወሓት በሚከተለው ዘረኝነትንና ጠባብነትን መርህ ባደረገው የፖለቲካ አመራሩ ምክንያት ሠርቶ መብላት ላልቻለው ፣ በስደት ምክንያት በበረሃ አውሬና በባህር አሣ ለሚበላው ፣ ከሐገር ቤት አልፎ የሌሎች ሐገራትን ወህኒ ቤቶችን ለሚያጨናንቀው፣ የእምነት ተቋሙ ተደፍሮ ሲኖዶስና መጅሊስ ለሚመረጥለት፣ የእምነት አባቶችም በአባይ ፀሐዬ በኩል ለሚሾምለት፣ በሃገር ቤት ለመኖር ለመረጠም በገዛ ሀገሩ የሁለተኛና ሦስተኛ ዜግነትን ተቀብሎ እንዲኖር  ለሚገደደውና ከፈጣሪ የተሰጠውና በአለም አቀፍ ተቋማት የተደነገገውን  ኢትዮጵያም የተቀበለቻቸውንና  የፈረመችባቸውን  ሰብአዊ መብቶቹን ለተገፈፈው ኢትዮጵያዊ እንደ ሀይለመድህን አይነት ብሶቱን በአለም አደባባይ የሚያሳይለትና የሚያጋልጥለት ሲያገኝ እንዴት ብሔራዊ ጀግናው አያደርገው!

እንደ መንግታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ዋና መስሪያ ቤት  (UNHCR) መረጃ በፈረንጆቹ 2013 ዓ/ም አጋማሽ ድረስ ብቻ ከአርባ ሁለት ሺህ (42,000) በላይ ኢትዮጵያውያን ስደት ጠይቀዋል ።

በውጭ መንግተስታት ዘንድ በተለይም እርዳታ በሚለግሱት ምእራባውያን ዲሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብት አክባሪ መስሎ ለመታየት የሚዳዳው የሕወሓት/ኢሕአዴግ መንግስት የደረሰበትን ፖለቲካዊ ኪሳራ ሂሳብ ለማወራረድ  “ሀይለ መድህን የአእምሮ በሽተኛ ነው” የሚል ዘመቻ ቢጀምርም ወንዝ ሊያሸጋግረው አልቻለም ።

በመቀጠል ህወሓት የወሰደው ርምጃ የመንግሥት ባለስልጣናትን ወደ ስዊዝ በመላክ የስዊዝ ባለሥልጣናትን አግባብቶና አሳምኖ ሀይለመድህንን ወደ ኢትዮጵያ ለመውሰድ መሞከር ነበር (የየመን መንግሥት በነፃነት ታጋዩ አንዳርጋቸው ፅጌ ላይ ያደረገውን እዚህ ላይ ማስታወሱ ተገቢ ነው) የስዊዝ ባለሥልጣናት ግን በፍፁም አይሞከርም የሚለው ቃል መልሳቸው ነበር።

ከዚህም በኋላ ሕወሓት የስዊዝ መንግሥት ባለሥልጣናትን ለማስፈራራት ይመስላል አንድ ከፍተኛ የህወሓት አባልና የመንግሥት ባለሥልጣን በድጋሜ ወደ ስዊዝ ላከ። የተላኩትም ሰሞኑን ከአንዲት የ14 አመት በአውስትራሊያ ነዋሪ ከሆነች ትውልደ ኢትዮጵያዊት “በሽልማት ያገኘችውን ” 20 ሚሊዮን የአውስትራሊያ ዶላር ተረከብኩ ያሉት የፌስቡክና ውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ  ቴድሮስ አድሐኖም ነበሩ   ፌብሩዋሪ 28 ቀን 2014 ዓ/ም። ስዊዞቹም እንኳን አንተና ባለራእዩ መሪያችሁ አፈሩን አራግፎ ቢመጣም ወይ ፍንክች አሏቸው መሰለኝ የፌስቡክ ሚንስትሩ ወደመጡበት ለመመለስ ሻንጣቸውን ከሸከፉ፣ ጠባቂዎቻቸውና አጃቢዎቻቸውን በቦታቸው መኖራቸውን ካረጋገጡ በኋላ ለመውጣት ሲዘጋጁ ከፕሮቶኮላቸው አንዱ ጠጋ ብሎ አንድ ነገር ሹክ አላቸው ። ቴድሮስ አድሐኖም የስዊዝ ባለሥልጣናትን ከሚያነጋግሩባት የስዊዝ የመንግሥት መቀመጫ በሆነችው በርን ከተማ ላይ ከሚገኘው መሥሪያ ቤት በቅርብ ርቀት ለጀግናው ሀይለመድህን ፍትህና ነፃነትን  የሚጠይቁ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሰላማዊ ሰልፈኞች ስላሉ ፣ ከመሥሪያ ቤቱ ሲወጡ እንዳያገኟቸው ጥንቃቄ እንዲደረግ ነበር የፕሮቶኮሉ መልእክት ።

ሰኔና ሰኞ የተገጣጠሙባቸው የማርክ ዙከርበርግ ቋሚ ደንበኛ ( valued customer)  ቴዲ በከፍተኛ አጀባና ጥንቃቄ ሰላማዊ ሰልፈኞቹ በሌሉበት አቅጣጫ አፈተለኩ። መቼም የፌስቡክ ደንበኛ ሆኖ መስራቹንና ባለቤቱን አሜሪካዊውን ማርክ ዙከርበርግን የማያውቅ የለም። ይኸው ለነ ቴድሮስ አድሐኖም ምስጋና ይግባና በያዝነው ሳምንት ፎርብስ መጽሔት ይፋ ባደረገው የአለማችን ሀብታሞች ደረጃ መሠረት ዙቢንገር በዚህ አመት ለመጀመሪያ ጊዜ ሃያዎቹ ቱጃሮች ውስጥ በመግባት የአለማችን 16ኛው ሃብታም ለመሆን ሲችል የሀብቱም መጠን 33.4 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል ። ድሮስ የተሰጣቸውን ከፍተኛ የስራ ኃላፊነት ገፋ በማድረግ አብላጫ  ጊዜያቸውን ፌስቡክ ላይ ፎቶ ሲለጥፉ የሚውሉና የሚያድሩ እንደ ቴድሮስ አይነት ደንበኞችን ይዞ  እንዴት ገቢው አያድግ!

የስዊዘርላንድ መንግሥት ተወካዮች ከህወሓት ባለሥልጣናት ጋር ስላደረጉት ተደጋጋሚ ውይይት ፣ ከኢትዮጵያውያንና ከተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን አውታሮች እንዲሁም ከሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ለሚደርሷቸው ጥያቄዎች ጠቅለል ያለ መልሰ ለመስጠት ያስችላቸው ዘንድ ሜይ 9 ቀን 2014  ዓ/ ም ለመንግሥት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ። በመግለጫቸውም:  የኢትዮጵያ መንግሥት በተደጋጋሚ ረዳት አብራሪ ሀይለመድህን አበራ ተላልፎ እንዲሰጣቸው ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ መደረጉን ፣ ወደፊትም ተላልፎ የሚሰጥበት ሁኔታ እንደማይኖር ፣ የፍርድ ሒደቱን በስዊዝ ፍርድ ቤቶች ችሎት እንደሚታይ፣ የስዊዝ መንግስትም የህግ ከለላ እንደሚያደርግለት፣ ያቀረበውም የፖለቲካ ጥገኝነት ጥያቄ ከፍርድ ሂደቱ መጠናቀቅ በኋላ እንደሚታይና አዎንታዊ መልስም እንደሚኖረው ( በስዊዝ ረዘም ላለ ጊዜ ለመኖር የሚያስችለውን ፈቃድ እንደሚያገኝ)  አስረግጠው ተናገሩ ።  በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የተገኙት የሀይለመድህን ጠበቆች ቡድን መሪ ዶ/ር ፊሊፕ ኩራ ( እሳቸው እንኳን ይችን ዶክተር መባል አይፈልጓትም የተገዛች ስላልሆነች ነው የተጠቀምኩባት) የስዊዝ መንግሥት ያሳለፈው ውሣኔ ተገቢ የሆነና ትክክለኛ መሆኑን ገልፀው አንድ ተከሳሽ በተመሳሳይ ክሶች በሁለት የተለያዩ ሃገሮች ችሎት ፊት ይቅረብ የሚል አለም አቀፍ ሕግም እንደሌለ ተናግረዋል ።

በድፕሎማሲው መንገድ እንዳልተሳካላቸው የተረዱት እነ ጭር ሲል አልወድም አዲስ ነገር ይዘን ብቅ ብለናል አሉ። ይሄኛውስ ምንድነው?  ይሄኛውማ  ሀይለመድህን ባይኖርም በሌለበት ( in absentia) ሞት፣ የእድሜ ልክ እስርና ሌሎችንም ጠንካራ ውሳኔዎችን በማሳለፍ አለም አቀፍ ዝናን ባተረፈው ፍርድ ቤታችንና የፍትሕ ስርአታችን አቃቤ ሕግ ክስ መስርቶበት እንዲያስፈርድበት እናደርጋለን የሚል ነበረ።

ፍትሕ ሚኒስቴር በረዳት አብራሪ ኃይለመድን አበራ ላይ  በከፍተኛው ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ክስ ሁለት ሲሆን፤ የመጀመሪያው በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 507/1/ ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፡-
‹‹…በዋና አብራሪ ፓትዮዝ ባርቤሪ አማካኝነት ከአዲስ አበባ በሱዳን በኩል ወደ ጣሊያን ሀገር ሮም ከተማ መንገደኞችን ለማድረስ በማጓጓዝ ላይ እንዳለ ዋናው አብራሪው የበረራ መቆጣጠሪያውን ክፍል ከውስጥ በመቆለፍ፣ ያለፍቃድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ አውሮፕላኑን በቁጥጥር ሥር በማድረግ የአውሮፕላኑ የበረራ ቡድን አባላት በሩን እንዲከፍት ሲጠይቁት አርፋችሁ የማትቀመጡ ከሆነ በአውሮፕላኑ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ ብሎ በማስፈራራት፤ እንዲሁም የአውሮፕላኑን የመዳረሻ አቅጣጫ ያለአግባብ በማስቀየር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ፈቃድ ውጭ ወደ ስዊዘርላንድ አየር ክልል ውስጥ በመግባት ተሳፋሪዎች እና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ሕይወት እና ደህንነት አደጋ ላይ እንዲወድቅ አድርጎ በመጨረሻ በጄነቭ ከተማ ውስጥ ያለመዳረሻው እንዲያርፍ በማድረጉ እና ተሳፋሪዎችን ለአደጋ በማጋለጡ በፈፀመው በሕገ-ወጥ መንገድ በጉዞ ላይ ያለን አውሮፕላን መያዝ ወይም ማገት›› የተከሰሰ መሆኑን ያትታል፡፡

በሁለተኛነት ክስ ደግሞ በዚሁ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 508/1/ ላይ ያለውን መተላለፍ የሚል ሲሆን፤ ክሱም በአጭሩ እንዲህ ይላል፡-
‹‹…ያለፍቃድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ አውሮፕላኑን በቁጥጥር ሥር በማድረግ የአውሮፕላኑ የበረራ ቡድን አባላት በሩን እንዲከፍተው ሲጠይቁት አርፋችሁ የማትቀመጡ ከሆነ በአውሮፕላኑ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ በማለት በማስፈራራት አውሮፕላኑን በድንገት እና በፍጥነት ሁለት ጊዜ ከፍ እና ዝቅ (dive) በማድረግ በአውሮፕላኑ ውስጥ ያሉትን የመንገደኞች ምግብ ማቅረቢያ ቁሳቁሶች እንዲገለባበጡ በማድረግ፣ የአውሮፕላኑን የመዳረሻ አቅጣጫ ያለአግባብ በማስቀየር፣ ከአትዮጵያ አየር መንገድ ፈቃድና እውቅና ውጭ ስዊዘርላንድ አየር ክልል ውስጥ በመግባት ስዊዘርላንድ ከተማ ጀኔቭ በመግባት አየር ላይ በማንዣበብ ከቆየ በኋላ እንዲያርፍ በማድረግ በፈፀመው በሕገ-ወጥ መንገድ በጉዞ ላይ ያለን አውሮፕላን አስጊ ሁኔታ ላይ መጣል ወንጀል ተከሷል፡፡›› ይላል ።

በፌ/አቃቤ ሕግ ብርሃኑ ወንድምአገኝ ፊርማ ለፍርድ ቤቱ የቀረበው ማመልከቻ ከስ ቻርጁን ጨምሮ አስራ አንድ ገፅ ሲሆን፤ የዋና አብራሪው፣ የአምስት የበረራ አስተናጋጆች እና የአራት ሰዎች ስም ዝርዝር በመስክርነት ተገልፆአል፡፡ በሰነድ ማስረጃነት ደግሞ አየር መንገዱ በ27/6/06 ዓ.ም ለፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ የጻፈው አራት ገጽ እና ሲቪል አቬየሽን በ21/6/06 ኃይለመድንን በተመለከተ የጻፈው ማብራሪያ ከነአባሪው ሁለት ገጽ ቀርቧል፡፡

የኃይለመድን አበራን የጤንነት ሁኔታ በተመለከተ አየር መንገዱ ለፌደራል ፖሊስ በላከው ደብዳቤ በስድስት ወር ውስጥ አምስት ጊዜ ያህል ለቀላል ሆድ ቁርጠት፣ ራስ-ምታት፣ ጉንፋንና ተቀምጥ ወደ ድርጅቱ ክሊንኪ ከመሄዱ ያለፈ ምን ችግር ያሌለበት ጠኔኛ እንደሆነ ገልፆአል፡፡ ሲቪል አቬሽንም በተመሳሳይ መልኩ በላከው ደብዳቤ አብራሪው አመታዊ የጤና ምርምራ አድርጎ እ.ኤ.አ. እስከ 22/12/2014 ዓ.ም ድረስ ጤነኛ መሆኑን ማረጋገጫ ሰርተፍኬቱን አድሶ እንደሰጠው አስታውቋል፡፡
( እዚህ ላይ በመጀመሪያ መንግሥት ኃይለመድህን የአእምሮ በሽተኛ ነው ብሎ እንደነበር ልብ ይሏል)
አየር መንገዱ ከዚሁ ጋር አያይዞ ሁለት መቶ ሀምሳ ሶስት ሺህ፣ ሶስት መቶ ሰላሳ ስድስት ብር ከአራባ ሁለት ሳንቲም (253,336.42) ዩሮ ኪሳራ እንደደረሰበት እና በቀጣይም ተጨማሪ ክፍያዎች እንደሚኖሩበት አሳውቋል፡፡

ህወሓት/ ኢሕአዴግ ራሱ ከሣሽ ራሱ ፈራጅ ሆኖ በሚተውንበት የፍርድ ቴአትር ቤት መታየት የጀመረው ድራማ የተጠበቀውን ተመልካች ማግኘት ካለመቻሉም በላይ የክሱም ስክሪፕት በጥሩ ፀሀፈ ተውኔት ስላልተፃፈ ቴአትሩን ለማየት ለታደሙትም ታማኝና ጥቂት የስርአቱ ልማታዊ ደጋፊዎችና ጋዜጠኞች የእንቅልፍ መድኃኒት ሆነባቸው ፣ አለም አቀፍም፣ ሐገር አቀፍም፣ ልማት አቀፍም ትኩረት አጣ።

አዲሱ ትኩረት መሳቢያ ቴአትር
—————————————-
ባሳለፍነው ሳምንት አውሮፕላን የተጠለፈበትን አንደኛ አመት ለማሰብም ይመስላል ሕወሓት አዲስ ዘዴ አግኝቻለሁ ይላል።
አዲሱ ዘዴ የተባለው ምንድነው ቢሉ፣ ኢንተርፖል በሚባል የአለም አቀፍ ፖሊስ ተቋም  በኩል “ሀይለመድህን አበራ የሚባል ረዳት  አውሮፕላን አብራሪዬ ጠፍቶብኛልና እባካችሁ ያያችሁ” የሚል የተማፅኖ ጥሪ ማሰማት ነው። በዚያውም የኢንተርፖል አባል መሆኔን እወቁልኝ ነው።  “የኢንተርፖል አባል መሆን ብርቅ ነው እንዴ?  ” አለ አሉ ይህን የሰማው ኮንስታብል ዶክሌ። ወደው አይስቁ !

ለማንኛውም “ረዳት አብራሪዬን ያያችሁ” ለሚለው በኢንተርፖል በኩል ለተሰራጨው ቀይ ማዘዣ( Interpol red notice) የመጀመሪያውን መልስ የሰጠችው ስዊዝ ነች ” አዎ እኔ አይቻለሁ እንቁልልጬ አይነት መልስ ።

ቅዳሜ ፌብሩዋሪ 27 ቀን 2007 ዓ/ም በፈረንሳይኛ ቋንቋ ለሚታተመው “ለ ማታ”  (Le Matin) ጋዜጣ አስተያየታቸውን የሰጡት የሀይለመድህንን ጉዳይ የሚያየው የኮንፌዴሬሽኑ አቃቤ ሕግ ቃል አቀባይ ጃኔት ባልመር “ለኢንተርፖል ተላልፎ ይሰጣል ወይ?  ለሚለው ጥያቄ በፍፁም አይሆንም አይሞከርም ነው መልሴ ብለዋል ።

ጃኔት ባልመር ይቀጥላሉ ” የ31 አመቱ ሀይለ መድህን በአሁን ጊዜ ስዊዝ ውስጥ በሕግ ጥላ ስር ይገኛል። በፍርድ ቤትም ጉዳዩ እየታየ ነው። በኢትዮጵያም ከአለም አቀፍ የሕግ ሂደት ባፈነገጠ ሁኔታና በስዊዝ ችሎት መቅረቡ እየታወቀ ክስ እንደተመሠረተበት ፣ እኛም አሳልፈን እንደማንሰጠው አሳውቀናል ። ኢንተርፖልም የቀይ መያዣ( ማሳሰቢያ) ጥሪውን ያስተላለፈው በኢትዮጵያ መንግሥት ጥያቄ መሆኑን አሳውቋል ። ” ይላሉ።

የሀይለመድህን ጠበቃ ፊሊፕ ኩራም ለዚሁ ጋዜጣ በሰጡት አስተያየት ” የኢትዮጵያ መንግሥት ሀይለመድህንን በይፋ ” ከሐዲ ” ብሎ ፈርጆታል ። በመሠረታዊውን የፍትህ ስርአት  (fundamental rule of law)  “አንድ ሰው በተመሳሳይ ክስ በሁለት የተለያዩ ችሎቶች መቆም የለበትም” የሚለውን በመፃረር ከኛም እውቅና ውጪ  በሌለበት ለመክሰስ ወስኗል ። በምን አይነት መልኩ ነፃ በሆነ የፍርድ ሂደት ጉዳዩ እየታየ እንደሆነም እኔ በበኩሌ የማውቀው ነገር የለም። የኢትዮጵያ መንግሥት በየጊዜው የተለያዩ ውጤት አልባ የማሰናከያ ቀመሮችን  እየፈጠረ ነው ” ይላሉ ።

የአቃቤ ሕጉ ቃል አቀባይ ጃኔት ባርመር “ለኢትዮጵያ መንግስት የአፀፋ መልስ የለንም። ለመንግስታችን የፖለቲካ ጥገኝነት ጥያቄ ያቀረበው  የሀይለመድህን አበራ  የፍርድ እጣ እዚሁ በጥሩ ሁኔታ ይወሰናል ። በርግጥ የፍርድ ሂደቱ ብዙም አልገፋም። ክፍት ችሎቶች የሉም። ምርመራዎች እንደቀጠሉ ናቸው ። ጉዳዩ ገና በምርመራ ላይ ያለ ስለሆነ ከዚህ በላይ ብዙ መናገር አልችልም  ” ብለዋል ።

ጠበቃ ፊሊፕ ኩራም “ሀይለ መድህን  በጣም ደህና ነው ። ስለ ፍርድ ሂደቱም  መናገር የምችለው:  እንዲህ መጓተቱ የተለመደ ባይሆንም ከንብረት ጋር የተያያዙ የተለያዩ መረጃዎችን ከተለያዩ ሐገሮች ለማግኘት ስንሞክርና መልስ ለማግኘት ረዘም ያለ ጊዜ መውሰዱ ነው። ልዩ ወደሆኑት  ቴክኒካዊ መረጃዎች  ስንመጣ ይህም ራሱን የቻለ የቴክኒክና የሳይንስ ምርመራ ይጠይቃል። በመጨረሻም የኮንፌዴሬሽኑ የህዝብ አቃቤ ሕግ  በመርህ ደረጃ 202 መንገደኞችን በሙሉ የሚያነጋግር ሲሆን አሁንም ከተሳፋሪዎቹ ስለራሳቸው  መረጃዎችን እየጠበቀ ይገኛል ። ” ብለዋል

የረዳት አብራሪ ሀይለመድህን አበራ ጉዳይ ከፌብሩዋሪ 17 ቀን 2014 ዓ/ም  እስከ ፌብሩዋሪ 28 ቀን 2015 ዓ/ም ድረስ የነበረውን የአንድ አመት ጉዞ ባጭሩ ይሄን ይመስላል።

ሀይለመድህን አበራ እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር ኦገስት 30 ቀን 1983 ዓ /ም  በጣና ሃይቅ ዳርቻ በምትገኘው ባህርዳር ከተማ ቀበሌ 03 ተወልዶ ያደገ ሲሆን የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በመጋቢት 28 ፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ ባህርዳር ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተከታትሏል።

ከፍተኛ ትምህርቱን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በአርክቴክቸር  ትምህርት ክፍል በመከታተል ላይ እያለና ለማጠናቀቅም አንድ ሴሚስተር ብቻ ሲቀረው በማቋረጥ ከልጅነት ጀምሮ ይመኘው የነበረውን የበረራ ትምህርት ለመከታተል የኢትዮጵያ አየር መንገድን የበረራ ት/ቤት ተቀላቅሏል። ፌብሩዋሪ 17 ቀን 2014 ዓ/ም አውሮፕላኑን ጠልፎ ጄኔቫ ስዊዘርላንድ እስካሳረፈበት ጊዜ ድረስ በአየር መንገዱ በረዳት አብራሪነት አገልግሏል። ከከጠለፋውም በኋላ የአየር መንገዱ የበረራ ክፍል ሃላፊ የነበሩት ካፒቴን ደስታ ዘሩ ከሥራቸው መልቀቃቸው ይታወቃል ።

በመጨረሻም በቅርቡ የኢትዮጵያ አየር ሐይል አባላት የሆኑ መኮንኖችና የበረራ ቴክኒሺያኖች በተለያዩ አቅጣጫዎች ሥርአቱን እየከዱ በመጥፋት ላይ መሆናቸውን እያየን ነው። በተለይም ወደ ጎረቤት ሐገር የኮበለሉት አንድ ተዋጊ ሄሊኮፕተር ይዘው መሆኑንም ራሱ መንግሥት በሚቆጣጠራቸው ሚዲያዎቹ  አረጋግጦልናል ።

ከ25 እስከ 30 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣውን ሄሊኮፕተር እና ለስልጠና ከፍተኛ ገንዘብ የፈሰሰባቸውን የበረራ ባለሙያዎችን ያጣውና በማጣት ላይ ያለው ህዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይና አመራሮቹ ረዳት አብራሪ ሀይለ መድህን አበራ ብቻ ገበናቸውን የገለጠባቸው  ለማስመሰል ወደ ምእራባውያን ሐገሮች ባለሥልጣናቱን መላክና ኢንተርፖልን ደጅ መጥናት ውሀ አያነሳላቸውም።

ምነው ዶ/ር  ቴድሮስ በነካ እጅዎ ወዳደጉባትና ወደተማሩባት ኣስመራ ጎራ ብለው የሄሊኮፕተሯንና የበረራ ባለሙያዎቿን ጉዳይንም ቢመክሩባትስ?
ከስዊዝስ  ኣስመራ አትቀርብዎትም?

The post የረዳት አብራሪ ሐይለመድህን አበራ ጉዳይና የአንድ አመት ጉዞው ባጭሩ -በጴጥሮስ አሸናፊ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

የትናንቱን የጭላሎ ተራራ የእሳት አደጋ በመቀስቀስ የተከሰሰው ግለሰብ በ10 ዓመት እስራት ተቀጣ

$
0
0

b921dbb2d1617779408d5dd6f6a9f717_Lአዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2007 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአርሲ ዞን በጢዮ ወረዳ በጭላሎ ተራራ ላይ ትናንት የተከሰተውን ቃጠሎ የቀሰቀሰው ግለሰብ በአስር ዓመት አስራት ተቀጣ። የወረዳው ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው  ችሎት የግለሰቡን ጉዳይ የተመለከተ ሲሆን፥ ተከሳሹ ቃጠሎውን መቀስቀሱን በማመኑ በ10 ዓመት እስራት ቀጥቶታል።

ቃጠሎውን የቀሰቀሰው ግለሰብ በዲገሉና ጢጆ ወረዳ ከቡቾ – ስላሴ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ወደ ቦሬ – ጭላሎ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ወደሚገኘው ወንድሙ ጋር በእንግድነት የመጣ መሆኑንም ፖሊስ ገልጿል። የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ኡርጋ ግዛው እንደገለጹት፥ ትናንት ጠዋት ረፋድ ላይ በተራራው ላይ በሚገኝ ደን ላይ የለኮሰው እሳት እስከ ምሽቱ ሁለት ሰዓት ከቆየ በኋላ ነው በቁጥጥር ስር ውሏል።

ቦሬ – ጭላሎ ቀበሌ ገበሬ ማህበር የተነሳው ቃጠሎ ወደ ሻላ – ጨብቲ፣ ቡርቃ – ጭላሎ እና ሀሮ – ቢላሎ የገጠር ቀበሌ በመዛመት በተፈጥሮ ሀብት ላይ ጉዳት ማድረሱንም ጠቁመዋል። በቀበሌዎቹ የተቀሰቀሰውን እሳት ለመከላከል የአካባቢው አርሶ አደሮች፣ ነዋሪዎች፣ የወረዳና ዞን ፀጥታ ኋይሎች ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ከዘጠኝ ሰዓታት በኋላ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቀዋል።

አደጋው በሰውና እንስሳት ላይ ጉዳት አለማድረሱ ተመልክቷል። በቃጠሎው የወደመውን የደን ይዞታ መጠን ለማጣራት ፖሊስ ከወረዳው ግብርናና ገጠር ልማት ጽህፈት ቤት ጋር እየሰራ ነው ብለዋል።

በጥበቡ ከበደ /ተጨማሪ መረጃ ከኢዜአ/

The post የትናንቱን የጭላሎ ተራራ የእሳት አደጋ በመቀስቀስ የተከሰሰው ግለሰብ በ10 ዓመት እስራት ተቀጣ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

አዲስ አበባ የሚገኘው ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ ከብርሃኑ ተዘራ ጋር በሰራው ዘፈን የተነሳ ከደህንነት ሃይሎች ማስፈራሪያ እየደረሰው መሆኑ ተሰማ * ስልኩ ተጠልፏል

$
0
0
ጃኪ እና ብርሃኑ ከሙዚቃ አቀናባሪው ሄኖክ ነጋሽ ጋር በስቱዲዮ ውስጥ

ጃኪ እና ብርሃኑ ከሙዚቃ አቀናባሪው ሄኖክ ነጋሽ ጋር በስቱዲዮ ውስጥ

ጃኪ የተቀረጸው ዘፈኑን በሄኖክ ነጋሽ ኮምፒውተር ሲያደምጥ

ጃኪ የተቀረጸው ዘፈኑን በሄኖክ ነጋሽ ኮምፒውተር ሲያደምጥ

(ዘ-ሐበሻ) ብርሃኑ ተዘራ (ብሬ ላላ) ከጃኪ ጎሲ ጋር የሠራው ወቅታዊ ዘፈን በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነትን ካተረፈ በኋላ አዲስ አበባ የሚገኘው ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ ስልኩ በደህንነቶች መጠለፉን እና በስር ዓቱ ሰዎችም ከፍተኛ ማስፈራሪያና ዛቻ እየደረሰው እንደሚገኝ ለድምጻዊው ቅርብ የሆኑ ወገኖች ለዘ-ሐበሻ አስታወቁ::

በዛሬው ዕለት ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ ፃፈው በሚል “ዘፈኑን ተሰርቄ ነው; ጃኪ የፖለቲካ ዘፈን አይዘፍንም” የሚል ጽሁፍ በፌስቡክ የተሰራጨ ሲሆን ይህ ጽሁፍ በአድናቂዎቹ እንጂ በጃኪ ጎሲ አለመፃፉን የደረሰን መረጃ ያመለክታል:: የጃኪ ጎሲ የግል 2 ፌስቡክ አካውንቶቹ ላይ ይህ ዜና እስከተዘገበበት ጊዜ ድረስ ከብርሃኑ ተዘራ ጋር ስለዘፈነው ዘፈን የሰጠው አስተያየት የለም:: ሆኖም የድምጻዊው አድናቂዎች ዘፈኑ ካለርሱ እውቅና ውጭ የተሰራ አድርገው የለጠፉት መረጃ ብዙዎችን ከማደናገሩም በላይ በተለይ ለአራት ቀናት ጃኪ ጎሲ በዋሽንግተን ዲሲ የሙዚቃ አቀናባሪው ሄኖክ ነጋሽ ጋር ሄዶ ከብርሃኑ ጋር ሲቀረጽ የተመለከቱ የዓይን እማኞች “ጃኪ ለምን ይዋሻል?” የሚሉ አስተያየቶችን በየሶሻል ሚዲያው እያሰራጩ ነው:: ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ በፌስቡክ ገጹ ምንም ያለው ነገር ባለመኖሩ አስተያየት ከመስጠት መቆጠብ ይሻላል የሚሉ ወገኖች; ጃኪ በስሙ በወጣ መግለጫ የተነሳ በስሙና በቀጣይ ሥራው ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ሳያደርስበት አቋሙን እንዲያሳውቅ ጠይቀዋል::

ጃኪ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ የሚገኝ ሲሆን የደህንነት ኃይሎች ስልኩን በመጥለፍ ከማን ጋር እንደሚያወራ እንደሚከታተሉት ዘፈኑን እንዲያስተባብል ከፍተኛ ጫና እያደረጉበት መሆኑን ለድምፃዊው ቅርብ የሆኑ ምንጮች ጠቁመዋል:: ጃኪ ከዚ ቀደም “ማን እንደ ሃገር” የሚል ነጠላ ዘፈን ሰርቶ የለቀቀ ሰሞን ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የድምፅአዊው የቅርብ ወዳጅ ተወዛዋዡ አብዮት መሃል ላይ ሰማያዊ የሌለበትን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ በኪሊፕ ሰርቶ ሲለቅ ጃኪም ይህን የሙዚቃ ክሊፕ ፌስቡኩ ላይ ሼር ሲያደርግ ደህንነቶች እንዴት ሕገመንግስቱ የማይፈቅደውን ባንዲራ በክሊፑ ላይ ትጠቀማለህ? በሚል ባደረሱበት ማስፈራሪያ ከፌስቡክ ገጹ ዘፈኑን ማስወጣቱን የሚጠቅሱት እነዚሁ የቅርብ ወገኖች አሁንም ደህንነቶች በሚያደርሱበት ወከባ ከፍተኛ ጫና ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል::

በጃኪ ስም አድናቂዎቹ የለጠፉት አደናጋሪ የፌስቡክ መልዕክት; ይህ በጃኪ የግል 2 ፌስቡክ አካውንቶች ላይ አልወጡም

በጃኪ ስም አድናቂዎቹ የለጠፉት አደናጋሪ የፌስቡክ መልዕክት; ይህ በጃኪ የግል 2 ፌስቡክ አካውንቶች ላይ አልወጡም


በዚህ ዘፈን ዙሪያ ድምፃዊው ብርሃኑ ተዘራን አግኝተን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም::

The post አዲስ አበባ የሚገኘው ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ ከብርሃኑ ተዘራ ጋር በሰራው ዘፈን የተነሳ ከደህንነት ሃይሎች ማስፈራሪያ እየደረሰው መሆኑ ተሰማ * ስልኩ ተጠልፏል appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አበል ካልተሰጠን ፍርድ ቤት አንቀርብም አሉ

$
0
0

newsበከሳሽ ኣቃቤ እና ህግ በተከሳሽ አቶ ኣስገደ ገ/ሥላሴ መካከል ሲደረግ በነበረው ክርክር ለምስክርነት የተጠሩት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ሊቀርቡ ባለመቻካቸው በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ ቢታዘዝም፤ ባለስልጣናቱ ከለመዱት ምቹ ህይወት አኳያ ማቅረብ ሳይቻል ቀረ።

የህወሀት የደህንነት ሰራተኛው ብስራት አማረ የመሰረተባቸውን ክስ ተከትሎ ላለፉት ሶስት ዓመታት ሲከራከሩ የቆዩት የቀድሞው የህወሀት ታጋይና የአሁኑ የሰማያዊ ፓርቲ አባል አቶ አስገደ ገብረስላሴ ላይ ክሳቸውን እንዲከላከሉ በፍርድ ቤት ብይን መሰጠቱ ይታወቃል።

ይህን ተከትሎ አቶ ኣስገደ ከጠሩዋቸው የመከላከያ ምስክሮች ውስጥ አራት ከፍተኛ የህውሃት አመራሮችና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ይገኙበታል። ለምስክርነት የተጠሩት እነኚህ ባለስልጣናት እነ አቶ ስብሃት ነጋ፣ አቶ ኣባይ ፀሃዬ፣ አቶ ስዩም መስፍን እና አቶ ኣርከበ ዕቁባይ ናቸው።

ባለስልጣናቱ ለመጁመሪያ ጊዜ ለ የካቲት 6 ቀን /2007 ዓመተ ምህረት የመከላከያ ምስክርነታቸውን ለመስጠት እንዲቀርቡ ትእዛዝ ቢደርሰዋቸውም ፤ እዚያው መቀሌ ከተማ ውስጥ እያሉ የዳኛውን ትእዛዝ በማጠፍ ሳይቀርቡ መቅረታቸውን አቶ አስገደ ገልጸዋል።

እንደገና ለሁለተኛ ጊዜ ለየካቲት 13 ቀን 2007 ዓመተ ምህረት በፖሊስ እንዲቀርቡ ዳኛዋ ቢያዙም፤ በድጋሚ እዚያው መቀሌ እያሉ የሉም ተብለው ሳይቀርቡ ይቀራሉ።

ለ3ኛ ጊዜ ለየካቲት 24 ቀን 2007 ዓ/ም በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ ሲታዘዝ ፖሊስ ቅድመ ሁኔታ ማቅረቡን ያመለከቱት አቶ አስገደ፤ ከቅድመ ሁኔታዎቹም አንዱ ተጠርተው ሲመጡ ከፍተኛ የሃገር ባለስልጣናት ከመሆናቸው አኳያ በሸራተን አዲሰ ደረጃ ባለ ሆቴል ማረፍ ስላለባቸውና በመቀሌ ያለው የዚያ ተመሳሳይ ሆቴል “ፕላኔት ሆቴል” በመሆኑ፤ ምስክር ጠሪው አቶ አስገደ በፕላኔት ሆቴል ለየአንዳንዳቸው ከነ ሁለት ኣጃቢዎቻቸው የአልጋ ዋጋ ሊከፍሉ ይገባል የሚል እንደሆነ ገልጸዋል።

ባለስልጣናቱ ከዚህም በተጨማሪ በከፍተኛ ፕሮቶኮል ማለትም በቪ አይ ፒ ደረጃ የኣየር ትኬት ከነ ኣጃቢዎቻችን ለመቁረጥ የሚያስችለን ገንዘብ፣ መቀሌ ለምንቆይበትም ቀናት የውሎ አበል ታስቦ ካልተሰጠን አንመጣም ብለውኛል ብሎ ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ በጽሁፍ ሪፖርት ማቅረቡን አቶ አስገደ ገልጸዋል። bአቶ አስገደ አስተያየታቸውን ሲያጠቃልሉ፦<<እዚህ ላይ የፖሊስ ሃላፊነት ምን መሆን ነበረበት? ተይዞ ይቅረብ የተባለው ድሃ ሰው ቢሆን ንሮ ምን ያጋጥመው ነበር?በኢትዮጰያ የህግ የበላይነት ተረጋግጧል ማለት ይህ ነውን?በማለት በ አጸንኦት ጠይቀዋል።

Source:: Ethsat

The post ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አበል ካልተሰጠን ፍርድ ቤት አንቀርብም አሉ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

119ኛዉ የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በዳላስ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

$
0
0

Kifle Mulat dallas

Obang dalas

Sey Adwa 8
(በስዩምና አሰፍ)
በዳላስና አካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እሁድ ዕለት (የካቲት 22, 2007) ታላቁን የአድዋ ድል በዓል በደማቅ ሁኔታ ሲያከበሩ ውለዋል። ይሄው በዳላስ ወጣቶች የተሰናዳው እጅግ የተዋጣለት፣ ያማረና የደመቀ በዓል ልዩ ልዩ ዝግጅቶች የቀረቡበት ሲሆን ሶስት ኢትዮጵያውያን በክብር እንግድነት ተገኝተው ንግግር አድርገዋል። በክብር እንግድነት የተገኙት ኢትዮጵያውያን፦

አቶ ኦባንግ ሜቶ (ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር – አኢጋን)
አቶ ክፍሌ ሙላት (አንጋፋ ጋዜጠኛና የቀድሞ ነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞች ማህበር ፕሬዚዳንት የነበሩ)
ፕሮፌሰር ሰለሞን አዲስ ጌታሁን (በሴንትራል ሚችገን ዩኒቨርስቲ የታሪክ መምህርና ተመራማሪ)

በዓሉ በወጣት ስዩም ወርቅነህ ፕሮግራም መሪነት የተካሄደ ሲሆን ከህጻነት ጀምሮ በሁሉም የዕድሜ ክልል የሚገኙ ወንዶችም ሴቶችም ታድመውበታል። በዳላስ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የጋራ መረዳጃ ማህበር ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ብርሃን መኮነን በበዓሉ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል።

የክብር እንግዶቹ በየተራ ባደረጉት ንግግር አድዋ የኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ ብሎም የመላው ጥቁር ህዝብ ድል መሆኑን አውስተዋል። በተለይ አቶ ኦባንግ ሜቶ ባደረጉት ንግግር አገራችን ቅኝ ሊገዛ የመጣውን ወራሪ የባዕድ ሃይል አያቶቻችን አሳፍረው መመለሳቸው ሁላችንንም የሚያኮራ ታሪክ ነው ካሉ በኋላ ከ100 ዓመት በፊት አያቶቻችን ያስመዘገቡትን የነጻነት ድል ስናስብ ዛሬ በሃገራችን ውስጥ በራሳችን መሪዎች በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን የነጻነት እጦትና የመብት ረገጣ ችላ ልንለው አይገባም ብለዋል። በሃገራችን ኢትዮጵያ ፍትህ፣ ነጻነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋፅዖ እናድርግ በማለት ታዳሚውን አሳስበዋል።

በመጨረሻም በወጣቶቹ የተዘጋጀው ኬክ በሶስቱም እንግዶች በአንድ ላይ ተቆርሶ ታዳሚዎች አስተያየታቸው እንዲሰጡ መድረኩ ክፍት ከተደረገ በኋላ አስተያየታቸው የሰጡ ሁሉም ወጣቶቹ ይህን የመሰለ በዓል በማዘጋጀታቸው አመስግነው ለወደፊቱ እንዲቀጥል አሳስበዋል። ወጣቶቹም በየአመቱ በአሉን ከዚህ በበለጠ በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር እንደሚያዘጋጁ ቃል ገብተው የፕሮግራሙ ፍጻሜ ሆኗል።

The post 119ኛዉ የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በዳላስ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ለአቶ ኤርሚያስ ለገሰ የሰጠው ምላሽ: ኤርምያስ ኤርምያስ ሆይ!

$
0
0

የኤርምያስ ለገሠን ‹ግልጽ ደብዳቤ› አነበብኩት፡፡ አንብቤው በሁለት ምክንያት ሳልጽፍለት ዘገየሁ፡፡ በአንድ በኩል ስለ ኤርምያስ ከነበረኝ የዋሕ ግምት የተነሣ ኤርምያስን ያህል ሰው ይህን ያህል አይሳሳትምና በቀጣዮቹ ቀናት በስሜ የወጣ ጽሑፍ ነው እንጂ የጻፍኩት እኔ አይደለሁም ይል ይሆናል ብዬ በመገመት፡፡ ጽሑፉ እንደወጣ ብዙ ሰዎች አሁን እኔ የምነግርህን ሲገልጡት ነበርና ትሰማቸዋለህ ብዬ አስቤ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የሐዲስ ዓለማየሁ የባሕል ማዕከል ባዘጋጀው ዐውደ ጥናት ላይ ልካፈል ወደ ደብረ ማርቆስ ተጉዤ ስነበር፡፡ 
daniel-kibret-300x207
ከደብረ ማርቆስ ተመልሼ ገጸ ድሮቹን ሳሥሥ ግን ኤርምያስ ከነ ስህተቱ ጸንቶ አገኘሁት፡፡ ገሥግሦ የመጣን ደኅና አድርገህ ጫነው ነውና ለዚህ ሰው መንገር ያለብኝ ነገር አለ ብዬ አሰብኩ፡፡

ይህን ‹ግልጽ ደብዳቤ› ኤርምያስ አይጽፈውም ያልኩት እንዲህ ጊዜና ሁኔታን የማያገናዝብ ሰው ነው ብዬ ስላልገመትኩት ነው፡፡ አንድን ጽሑፍ ለመጻፍ ሲል ብቻ የሚጽፍ ሰው አድርጌ ስላልገመትኩትም ነው፡፡ ያንን መጽሐፉን በዕውቀትና በመረጃ ስለመሰለኝ ‹ቅዳሴው አልቆብህ ቀረርቶ ትሞላበታለህ› ብዬ ስላላመንኩ ነው፡፡

ኤርምያስ ሆይ፤

ይሄ አሁን አንተ አይተህ የደነገጥክለት ጽሑፍ አንተ ባዳመጥከው ጊዜ (በ2007 ዓም) የቀረበ ጥናት አይደለም፡፡ ምናልባት ‹ምንትስ የሰማ ለት ያብዳል› ሆኖብህ ካልሆነ በቀር፡፡ ጽሑፉ የቀረበው ነሐሴ 25 ቀን 1999 ዓም አሜሪካ፣ ዴንቨር ኮሎራዶ ከተማ ተደርጎ በነበረው ሰባተኛው የአሜሪካ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ ነው፡፡ የተለቀቀው ደግሞ ከአንድ ወይም ከሁለት ቀን በኋላ www.tewahedo.org በተሰኘ ገጸ ድር ነው፡፡

በዚያ ጥናት ውስጥ ‹አክራሪነት› የተፈረጀው ከእምነት አንጻር ነው፡፡ አክራሪ እስላም ስልም ‹‹በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ ሆን ብሎ የጥፋት ዓላማ በመያዝ፣ የሕዝቡን አብሮ ተገናዝቦ የመኖር ሥርዓት በማፍረስ፣ አንዳንዴም የሌሎችን ዓላማ በማንገብና የቤት ሥራ በመውሰድ የተሠማራውንና እስልምናን ሽፋን የሚያደርገውን የጥፋት ኃይል ነው›››፡፡ ክርስቲያኖች ሁሉ ቅዱሳን ናቸው እንደማልለው ሁሉ ሙስሊሞች ሁሉ አክራሪዎች ናቸው ብዬ አላውቅም፡፡ አልልምም፡፡ ምክያቱም፣ ስላልሆነ፡፡

እስከ 2002 ዓ.ም ያለው ወቅት ማለት ደግሞ አንተ ራስህ በመጽሐፍህ እንደነካካኸው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ለማየት በማይፈልጉ ‹አክራሪ ሙስሊሞች› ቦታዋን የመንጠቅ፣ ካህናቷን የማረድ፣ ገዳማቷን የማቃጠል፣ ቅዱሳት መጻሕፍቷን የመዝረፍና ወደ ባዕድ ሀገር የማሻገር እኩይ ተግባር ይከናወን የነበረበት፣ እንዲያውም ሁኔታው ራሱ ጫፍ የደረሰበት ጊዜ ነበር፡፡

አንተ ዛሬ ስትወጣ በሌሎች ብቻ አመካኘኸው እንጂ በአዲስ አበባ አየር ጤና ኪዳነ ምሕረት የጥምቀት ቦታ ክርክር ጊዜ የመንግሥትን ሥልጣን ይጠቀሙ ከነበሩት ሰዎች አንዱ ነበርክ፡፡ በወቅቱ እኔ የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያዎች ኃላፊ ነበርኩ፡፡ ጉዳዩን ከእግር እስከ ራሱ ዐውቀው፣ እከታተለውም ነበር፡፡ መረጃዎቹንም ከየአቅጣጫው እናገኝ ነበር፡፡ አጠናቅረንም በጋዜጣ እናወጣ ነበር፡፡ በዚያም ምክንያት አያሌ ጫናዎችን ካደረሱብን ሰዎች አንዱ አንተ ነበርክ፡፡ ቢሮህ አስጠርተህን ቤተ ክርስቲያኒቱንና የፈረደበትን አማራ ምን ብለህ እንደተሳደብክ  የምናውቀው አንተ እና እኛ ነን፡፡

ከአሰቦት መነኮሳት የ1984 ዓም መታረድ በኋላ በሚዲያ ዋና ክፍል እኔና ጓደኞቼ ከሠራናቸው ሥራዎች መካከል አንዱ አክራሪ ሙስሊሞች በቤተ ክርስቲያኒቱ ከጥንት እስከ ዛሬ ያደረሱትን፣ ሊያደርሱትም ያሰቡትን መረጃ ማሰባሰብ ነው፡፡ አንዳንዶቹን በቦታው ተገኝተን፣ ሌሎቹን ከቦታው በሚመጡ መረጃዎች፣ የቀሩትንም ከተለያዩ የመረጃ ምጮች አሰባስበናቸው ነበር፡፡ ከሚመለከታቸው የውጭ ዩኒቨርሲቲዎችና የመረጃ ምንጮችም በውድ ዋጋ የገዛናቸው ነበሩ፡፡

በነገራችን ላይ ያ ጽሑፍ በፕሮጀክተር ታግዞ ቀርቦ ስለነበር የመረጃ ምንጮቹን የሚያሳየው የጎንዮሽ ማስተዋሻን ማንበብ አላስፈለገም፡፡ ለዚህ ነው ምንጩን የድምጹ መልእክት ላይ ያላገኘኸው፡፡ የድምጹን መልእክት የለቀቅኩትም እኔ አልነበርኩም፡፡ የኦርቶዶክስን ትምህርቶች በመረጃ መረብ በመልቀቅ የሚታወቀው www.tewahedo.org የተሰኘ ገጸ ድር ነው፡፡ ዛሬም በዚሁ ገጸ ድር ላይ ስላለ ማየት ትችላለህ፡፡ ወይም አዘጋጁን በገጸ ድሩ ላይ ባሠፈረው የመመየሊያ አድራሻው(email)ብትጠይቀው የሚነግርህ ይመስለኛል፡፡

አንተን ወደ ባሰው ስሕተት የወሰደህ የተሟላ መረጃ ሳታገኝና ለማግኘትም ሳትፈልግ ወደ ድምዳሜ መንደርደርህ ነው፡፡ የመጀመሪያው፣ እኔ ጥናቱን በ1999 ዓም ዴንቨር ኮሎራዶ፣ በ2000 ዓም አዲስ አበባ ደብረ ገሊላ ዐማኑኤል ቤተ ክርስቲያንና በዮርዳኖስ ሆቴል (ማኅበሩ ስለ ሚሊኒየም ባዘጋጀው ጉባኤ) ካቀረብኩት በኋላ ነው ‹ሽመልስ ከማል ሠራው› ያልከው ጥናት ለመንግሥት የቀረበው፡፡ ያ ጥናት ለመንግሥት አካላት ሳይለዋወጥ መቅረቡን በወፍ በረር እናውቅ ነበር፡፡ ስለዚህም የተከተለ ከቀደመ ይወስዳል እንጂ የቀደመ ከተከተለ አይወስድምና ‹ቃላት ሳይቀየሩ የቀረበው› እኔ ያቀረብኩት ጽሑፍ እንጂ በእናንተ ስብሰባ ላይ የቀረበው ጽሑፍ ወደ እኔ መጥቶ ሊሆን አይችልም፡፡ አንተ ራስህ በመጽሐፍህ ውስጥ አድንቀህ የጠቀስከው የአቡነ ሳሙኤል መጽሐፍኮ ይህንን ዋቤ አድርጎ የተጻፈ ነበር፡፡ እርሳቸውም ‹ከሽመልስ ከማል ወስደው› ነው ልትል ነው?

ሁለተኛው ስሕተትህ ቤተ ክርስቲያኒቱንና የቤተ ክርስቲያኒቱን ልጆች የምታይበት ዓይንህ ዛሬም አለመስተካከሉን የሚያሳየው ስሕተት ነው፡፡ ይህቺ ቤተ ክርስቲያን የሚቆረቆሩ ብቻ ሳይሆኑ መሥዋዕት ሆነውም ታሪክ የሚሠሩ ልጆች አሏት፡፡ እነዚያ ልጆች ናቸው አይገቡ ገብተው እነዚያን መረጃዎች የሰበሰቧቸው፡፡ አንዳንዶቹን መረጃዎች ለማግኘት እንደ ሠለስቱ ደቂቅ በእሳት ውስጥ ማለፍን ይጠይቅ ነበር፡፡ አንተና ሌሎቻችሁም የደነገጣችሁት ‹‹ሰው በቅንዐተ እምነት ተነሣስቶ እንዲህ አይሠራም፣ ሌላ ከጀርባው አንድ ነገር አለ›› ብላችሁ ስለምታምኑ ነው፡፡

በበሻሻ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ጅማ ውስጥ በጥቅምት 1998 ዓም አክራሪ ሙስሊሞች በየዋሐን ምእመናንና ካህናት ላይ የፈጸሙትን ግድያ ሕዝቡ ሲሰማኮ አንተና ሌሎቻችሁም ጣታችሁን እኛ ላይ ጠቁማችሁ ስንት ቀን እሥር ቤት አመላልሳችሁናል፡፡ አንተ ራስህ በመጽሐፍህ የገለጥከው ራስህ ቆመህ ያስፈረስከውን ቤተ ክርስቲያን በተመለከተ በድፍረት መጀመሪያ የዘገብነው በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ ላይ ነበር፡፡ ያኔ ምን እንዳላችሁን ታውቃለህ፡፡

ሦስተኛው ስሕተትህ ‹የዶክተር ሺፈራው ጥናት ለምን በአንተ ጥናት ውስጥ አልቀረበም?› የሚለው ነው፡፡ ለምን ይቀርባል? እኔኮ የራሴን ጥናት ሠርቼ በራሴ መድረክ ላይ ነው ያቀረብኩት፡፡ 1999 ዓም ከ2001 ዓም በኋላ የሚመጣ ነው ካላልከኝ በስተቀር፤ በኋላ የተደረገ ጥናት እንዴት ተደርጎ ነው በፊት በተሠራ ጥናት ውስጥ የሚካተተው?

የዛሬ 8 ዓመት ጥናቱ ሲሠራ ያገኘናቸውንና ያመንባቸውን መረጃዎች ተጠቅመናል፡፡ ያ ማለት ግን ሁሉን ዐውቀን ነበር ማለት አይደለም፡፡ አንተ ጉዳዩን ሲያባብሱ ነበሩ ያልካቸው ባለ ሥልጣናት አክራሪነትን ሲመሩትና ሲያቀጣጥሉት ነበር ካልክ መረጃውን በበቂ ሁኔታ አንተ በቦታው የነበርከው ንገረን፡፡ ከዚያ ውጭ መከላከያ ሠራዊት ያደረገውን ጥረት ግን በአካል በመገኘት ጭምር ዐውቀዋለሁና ልዋሽ አልችልም፡፡ የተወሰኑ የመንግሥት አካላት የወሰዱትን በጎ ርምጃም ልዋሸው አልችልም፡፡ እውነት ነበርና፡፡

እጅግ ያስገረመኝ ደግሞ ‹በጥናታዊ ጽሑፍህ አሁን ያለውን የሙስሊሞች ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለምን አላነሣህም?› ብለህ የጠየቅከው ጥያቄ ነው፡፡ ለመሆኑ ይኼ እንቅስቃሴ ጥናቱ በቀረበበት በ1999 ዓም  ተነሥቶ ነበር? ወይስ ለምን ወደፊት ይመጣል ብለህ ትንቢት ለምን አልተናገርክም ማለትህ ነው? ስሜ ነው እንጂ እኔኮ ነቢይ አይደለሁም፡፡ እንዲያ ከሆነ ደግሞ አንተም ስምህ የነቢይ ነውና በኋላ በኢሕአዴግ ውስጥ ደረሰ የምትለውን ችግር ቀድመህ ዐውቀህ ለምን ከአባልነት አልታቀብክም? የሚል ጥያቄውን ስትመልስ እመልስልሃለሁ፡፡

ስለ ‹ስደተኛው ሲኖዶስ› አቋሜን በተደጋጋሚ ገልጫለሁ፡፡ የፖለቲካውን ገጽታ አንተ ንገረን፡፡ በክርስትናው ግን መንጋውን ጥሎ የሚሄድን እረኛ ጻድቅ የሚያሰኝ ነገር ስላላገኘሁ ነው፡፡ ‹የቅዱስ ሲኖዶስ መንበሩ አዲስ አበባ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ነው› የሚለው የቅዱስ ሲኖዶስ ደንብ የወጣውኮ አሁን በስደት ያሉት አንጋፋዎቹ አባቶች አዲስ አበባ እያሉ በ1972 ዓም ነው፡፡ ያንን የማክበር ግዴታ የሁሉም ነው፡፡ ‹አባት አንጂ መንበር አይሰደድም› የሚለው ደግሞ ዛሬም ነገም አቋሜ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች እንኳን ተሰድደው ፓርቲ አቋቋሙ እንጂ መንግሥት አላቋቋሙም፡፡ በምን ቀኖናዊ መብት ነው ተሰድዶ መንበር ማቋቋም የሚቻለው? ከመንበሩ ውጭ ሆኖ ሀገረ ስብከቱን ያስተዳደረ አንድ ሲኖዶስ እስኪ በታሪክ ይጠቀስልኝ? እኔ አንተን ጥቀስ ብዬ አላስቸግርህም፡፡

‹መንግሥት በቅዱስ ሲኖዶስ ጫና ማድረጉና ጣልቃ መግባቱ› ተቀባይነት የሌለውና የምእመናንን ገድል የሚጠይቅ መሆኑ ባይካድም አሁን ያሉትን አበው ብቻ የሚመለከት ወቀሳ ግን አይደለም፡፡ ለቤተ ክርስቲያናችን አንዱ የዘመኑ ተግዳሮት ብሔራዊ ሲኖዶስ ከተቋቋመ ጀምሮ ከመንግሥት ተጽዕኖ ነጻ የሆነ ሲኖዶስ አለመኖሩ ነው፡፡ ያ ማለት ግን ለእምነታቸው የሚሞቱ፣ ለእውነት የሚሟገቱ አበው በቅዱስ ሲኖዶስ ውስጥ የሉም ማለት አይደለም፡፡ አንተ ራስህ ይህንን በመጽሐፍህ ስለጠቀስከው ለቀባሪ አላረዳም፡፡

እዚህ ላይ ግን በግልጽ ልነግርህ የምችለው የመንግሥት ባለ ሥልጣናት በተወሰኑ አባቶች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርሱ ይችሉ ይሆናል እንጂ አንተ እንዳልከው ቅዱስ ሲኖዶሱን እስከ ማሽርከር የሚደርስ ዐቅም ፈጽሞ የላቸውም፡፡ቢኖራቸው ኖሮ አንተ ራስህ ተገኝተህ የታዘብከውን የአባቶች ጥንካሬ ማየት አትችልም ነበር፡፡ በ2006 ዓም በሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ የተገኙትን የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ተወካዮች በመረጃና ማስረጃ ሲወጥሩ፣ እምነታቸውን ሲመሰክሩና ያለ ፍርሃት ሲናገሩ እኔ ራሴ አባቶቼን በዓይኔ አይቻቸዋለሁ፡፡ ይህን ያደረጉት አሜሪካ ሆነው አይደለም፡፡ በቢላዋው ሥር ሆነው እንጂ፡፡

‹ለምን አሁን ቀረበ?› ብለህ የጠየቅከኝ በ2000 ዓም ቢሆን ኖሮ አብራራልህ ነበር፡፡ ጥናቱ የቀረበው በ1999 ዓም፣ አንተ ጥያቄውን ያነሣኸው ደግሞ በ2007 በመሆኑ ‹ይለፈኝ› እልሃለሁ እንደ ጋይንት ሰው፡፡

በመጨረሻ ኤርምያስ ሆይ

‹ብለነው ብለነው የተውነው ነገር

ባሏ ትናንት ሰምቶ ታንቆ ሊሞት ነበር›

የተባለው ደርሶብህ፤ ማጣሪያና ማብራሪያ ሳታገኝ ወርደህ በመጻፍህ፤ ገረመኝም አሳዘነኝም፡፡ የገረመኝ ‹አንተን የሚያህል› ብዬ የማስብህ ሰው ሁለቴ እንኳን ሳይለካ ለመቁረጥ በመቸኮሉ፤ ያሳዘነኝ ደግሞ ‹ኤርምያስ ሌላውንም ነገር የሚነግረን እንዲህ አመክንዮአዊ ሐሰት ይዞ ነው ማለት ነው› እንድል ስላደረገኝ ነው፡፡ አመክንዮአዊ ሐሰት ማለት በአቀራረቡ ተጠየቃዊ የሆነ፣ ነገር ግን በስሕተት መረጃዎች የተሞላ ማለት ነው፡፡

በመጨረሻ ዳዊት ለሳዖል የዘመረውን መዝሙር ልጋብዝህ

‹ኃያላን እንዴት ወደቁ›

 

The post ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ለአቶ ኤርሚያስ ለገሰ የሰጠው ምላሽ: ኤርምያስ ኤርምያስ ሆይ! appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ልማታዊው ጓደኛዬ –ከዋስይሁን ተስፋዬ

$
0
0

የካቲት 26 ቀን፣ 2007 እ.ኢ.አ.

ጥንት አባቶቻችን እንደሚሉት “ነገርን ነገር ያነሳዋል…” ነውና፤ በአንድ ያልታሰበ አጋጣሚ እንደቀልድ ከአንድ የምወደው የቀድሞ ወዳጄ ጋር በዋዛ ፈዛዛ ያደረኳቸው ጨዋታዎች፤ እውነትም በምንወዳትና በምንሳሳላት ሃገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት እየተከናወነ የሚገኘውን ነባራዊ እውነታ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ስለመሰለኝ፤ ይህንኑ ለአንባቢያን ፍርድ ማቅረብን ወደድሁ። ነገሩ እንዲህ ነው…!

የዛሬ ሁለት ወር አካባቢነው። ከአመታት በፊት፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሳለን የቅርብ ወዳጄ የነበረ ጓደኛዬን ፌስቡክ ላይ ባጋጣሚ አገኘሁት። ለአመታት ሳንገናኝ በመቆየታችን ናፍቆታችንን ለመወጣት ይመስላል፤ በጓደኝነት ያሳለፍናቸውን ጊዜአት በትዝታ መልክ እያስታወስን ስናወጋ ለሳአታት ቆይተን ነበር። ይህ ወዳጄ ዝምተኛ የሚባሉ ከነበሩ ተማሪዎች መካከል የሚመደብ ሲሆን፤ እንደኔ በሚቀርቡት ወዳጆቹ ግን በጨዋታ መሃል ሳይታሰብ ጣል በሚያደርጋቸው አስቂኝ ቃላቶቹ ይታወቃል። እንደነገረኝ ከሆነ በአሁኑ ሰአት ከዩኒቨርሲቲ በተመረቀበት ሙያ እያገለገለ ሳይሆን፤ ያዋጣል ብሎ ባሰበው የንግድ ስራ ላይ ተሰማርቶ እየሰራ ይገኛል። በመሆኑም አንድ መለስተኛ ህንፃንና ሁለት የንግድ ድርጅቶችን በባለቤትነት ያስተዳድራል። ይህ ወዳጄ ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባትም ሆኗል። በኔ ግምት እንደተመረጡት ቁንጮ ባለስልጣናት የናጠጠ ሃብታም ባይሆንም፤ ጥሩ ኑሮን ይኖራሉ ከሚባሉት ጥቂት ዜጐች ተርታ የሚመደብ ይመስለኛል።

ባልሳሳት ለአንድ ሰአት ያክል ፌስቡክ ላይ በፅሁፍ በመመላለስ እንዳወጋን፤ ጓደኛዬ “የበለጠ እየተያየን ብናወጋ የተሻለ ይሆናል” በሚል እሳቤ፤ ወደ ስካይፕ እንድንሄድ ጠየቀኝ። እኔም ተስማምቼ ጨዋታችንን በስካይፕ ቀጠልን። በአካል ስመለከተው በፅሁፍ የነገረኝ የኑሮ ደረጃ ላይ እንዳለ ሰው የተመቸው አይመስልም። በውስጤ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ብዬ እያሰላሰልኩ ጨዋታችንን ቀጠልን።

ለአመታት የተለየሁትንና ያላየሁትን ወዳጄን እያየሁት ማውራት በመቻሌ እጅግ ተደስቼ የነበረ ቢሆንም፤ ለጥቂት ደቂቃዎች ከተጫወትን በሗላ ምናልባትም ለወዳጄ አስጊ ሊሆን የሚችል ነገር ትዝ አለኝ። ነገሩ እንዲህ ነው፤ የዛሬ ሁለት አመት አካባቢ አብሮኝ የሚሰራ አንድ ሐበሻ “ኢትዮጵያ ውስጥ በስካይፕ መነጋገር በህግ ያስቀጣል።” የሚል ህግ እንደተደነገገ የነገረኝን አስታወስኩ። መረጃውን ያካፈለኝ ባልደረባዬ እንደኔው ተሰዶ በውጭ ሃገር የሚኖር ስለነበረ ትክክለኛ ስለመሆኑ እርግጠኛ ባልሆንም፤ ጉዳዩ ለወዳጄ ደህንነት ወሳኝ እንደሆነ ስለተረዳሁ፤ ስለመረጃው እውነትነት እርግጠኛ አለመሆኔን በመናገር እንዲያረጋግጥልኝ በጥያቄ አቀረብኩለት። “እኔምልህ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በስካይፕ መነጋገር ክልክል አይደለም እንዴ !?” የመንግስታችንን አይምሬነት ስለምገነዘብ፤ እርሱም ቢያንስ ከእኔ በላይ ይጨነቅበታል ብዬ ያመንኩበት ወዳጄ፤ ፈጠን ብሎ “ባክህ እርሳው፤ መንግስታችን የሚያወጣው ህግ ከጐኑ ላጲስ አለው” ቢለኝ በጣም ተገረምኩ።

የተናገረውን በሚገባ የሰማሁት ቢሆንም፤ በመልሱ ግራ ስለተጋባሁ “ምን አልከኝ!?” አልኩት። ጓደኛዬም ነገሩ እንግዳ እንደሆነብኝ ስለተረዳ ጉሮሮውን ሳል ሳል አደረገና “ስለዚህ ጉዳይ የማያውቅ ኢትዮጵያዊ አለ ብዬ አስቤም አላውቅ። እውነትም ከሃገር ርቀሃል ጃል!” በማለት ጨዋታውን ቀጠለ። “በአሁኑ ሰአት ኢትዮጵያ ውስጥ የተደነገገ ማንኛውም ህግ ላጲስ ከጐኑ አለ እኮ ነው የምልክ! አልሰማህም እንዴ!?” ብሎ በመገረም ጥያቄዬን በጥያቄ መለሰልኝ። ወዳጄ አሁንም ያን ቀልዱን አለመተዉን ለቅፅበት አሰብ አረኩና፤ ጨዋታውን እንዲቀጥልልኝ ስለፈለኩ “ኧረ በጭራሽ አልሰማሁም፤ ደግሞ ይህ ምን ማለት ይሆን!?” ፤ “አይ አንተ ልጅ አሁንም ቀልድህን አልተውክም ማለት ነው!?” ጠየኩት። ወዳጄም ፈገግ ካለ በሗላ፤ ቀጠለ “አየህ ባሁኑ ሰአት እዚህ ሃገር ላይ ማንኛውም ወንጀል ብትሰራ በህግ አትቀጣም።”፤ “ማለቴ የመንግስታችንን አስተዳደር እስካልተጋፋህ ድረስ።”
ብዙ ጊዜ በጨዋታ መሃል ቀልድ ቢጤ ጣል ማድረግ ስለሚወድ፤ አሁንም ይህንኑ የሚያደርግ መስሎኝ የነበረ ቢሆንም፤ እርሱ ግን ፊቱን አኮሳትሮ፣ ግንባሩን አቀጭሞ ንግግሩን ቀጠለ፤ “መንግስታችን ከህገ መንግስቱ ጀምሮ በርካታ ህጐችን በወረቀት ላይ በግልፅ አስፍሯል። ነገር ግን እነዚህን ህጐች ከመንግስት ጀምሮ ማንም አያከብራቸውም፤ አይተገብራቸውምም።” የሚያጫውተኝ ቁምነገር በቀልዱ የማቀው የቅርብ ወዳጄ የነበረ ሰው ያልተጠበቀ ሲሬስነት ጋር ተጣምረው፤ ለንግግሩ ሙሉ በሙሉ አትኩሮቴን እንድሰጥ ስላስገደዱኝ፤ ሳላስበው በተመስጥኦ ማዳመጥ ጀመርኩ። እርሱ ግን መናገሩን አላቋረጠም። “መንግስትን ጨምሮ ሁላችንም ህግ እንጥሳለን፤ ምክንያቱም የምንጠየቅበት መች እንደሆነ እናውቃለና!” በአትኩሮት አይን አይኔን እያየ ንግግሩን ቀጠለ፤ “እኔ ራሴ በቀን ብዙ ህጐችን እጥሳለሁ፤ ይህን ደግሞ መንግስት በሚገባ ያውቃል፤ ግን ማንም ጠይቆኝ አያውቅም።” “አየህ እኔ ልማታዊ ዜጋ ነኝ፤ ልማታዊ ዜጋ ታውቃለህ!?” በማለት ያልጠበኩትን ጥያቄ ሲያቀርብልኝ ከእንቅልፌ የነቃሁ ያክል፤ “ኧረ በጭራሽ! ቀጥል!?” አልኩት። በርግጥ በአሁኑ ሰአት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች “ልማታዊ ጋዜጠኞች” እንደሚባሉ ስለማውቅ፤ “ልማታዊ ዜጋ” ምን እንደሆነ መገመትና መናገር እችል ነበር። ነገር ግን ጨዋታውን የሚያቋርጥብኝ ስለመሰለኝ ባጭሩ “ቀጥል” አልኩት።

ጨዋታውን ለመስማት መጓጓቴ እንዳስገረመው ከፊቱ ላይ በሚነበብ መልኩ ቀና ብሎ ካየኝ በሗላ ንግግሩን ቀጠለ፤ “አየህ እኔ ‘ልማታዊ ዜጋ’ ስለሆንኩ፤ በመንግስታችን ስራ ጣልቃ አልገባም። ያሻውን ቢያደርግ አርሱ የኔ ጉዳይ አይደለም፤ አይመለከተኝምም።” እያዳመጥኩት እንደሆነ ከረጋገጠ በሗላ በተመስጥኦ ጨዋታውን ቀጠለ፤ “ገባህ ከእኔ የሚጠበቀው፤ የተፈቀደልኝን ብቻ እየሰራሁ እስከተፈቀደልኝ ድረስ ‘በሠላም’ መኖር ብቻ ነው። እንዳልኩህ በመንግስት የስራ ጉዳይ ውስጥ በፍፁም ጣልቃ መግባት የለብኝም፤ የኔ ስራም ለዚህ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ነው፤ አለበለዚያ የምሰራቸው ወንጀሎች ያስጠይቁኛል።”

ለአፍታ አቀርቅሮ ካሰበ በሗላ፤ አትኩሮ እየተመለከተኝ ጨዋታውን ቀጠለ፤ “ሌላው የኔ ስራ ደግሞ፤ ምርጫ ሲደርስ መንግስትን መምረጥ፤ ዜጐች ቢበደሉ፤ ሃገር ቢቆረስ፤ ንፁህ ዜጋ ወንጀለኛ ተብሎ ቢፈረድበት፤ ሌላም ሌላም፤ ሁሉም ለኔ ጉዳዮቼ አይደሉም። ከኔ የሚጠበቀው መንግስት የሚፈልገውን እየሰራሁና እያስተጋባሁ ኑር እስከተባልኩ ድረስ መኖር ብቻ ነው።” እየሰማሁ ያለሁት ጉዳይ በጣም ግራ ስላጋባኝ፤ በአንድ በኩል የሰው ልጅ እንዴት በእንደዚህ የተሳሰ ሁኔታ መኖር ይችላል!? መለስ እልና ደግሞ ጓደኛዬን ድሮ ሳውቀው አደለም የማያምንበትን፤ አምኖ የተቀበለውን እንኳ በተገቢው መፈፀም እንደሚያጨናንቀው ነበር፤ አሁን ታዲያ ምን ነክቶት ይሆን!? ሌሎች ብዙ ጥያቄዎችን በውስጤ እያሰላሰልኩ፤ የራሴ አለም ውስጥ ሳላስበው ሰጥሜ አዳምጠው ነበር። እርሱ ግን ንግግሩን ቀጥሏል፤ “መንግስት ኢኮኖሚው በሁለትም በሶትም ዲጂት አደገ ካለ፤ እኔም ያንን አስተጋባለሁ፤ ቁጥር የኔ ጉዳይ አይደለም።”

በዝምታ አንገቱን አቀርቅሮ ለጥቂት ሴኮንዶች ጨዋታውን ሲያቋርጥብኝ፤ ያልሆኑ ጥያቄዎችን አምጥቼ ወዳጄን ያስከፋሁት ስለመሰለኝ፤ ነገሩን ወደ ሌላ ጨዋታ አቃልዬ ለማስቀየር በማሰብ፤ እሺ እና ቤተሰብ እንዴት ነው ባክህ!? አልኩኝ። እርሱ ግን ቀና ብሎ አይቶኝ ጨዋታውን ቀጠለ፤ “ንግድ ውስጥ እንዳለሁ ነግሬሃለሁ፤ አይደል!?” አለኝ። ደንገጥ ብዬ፤ በፍጥነት “አዎን ነግረኸኝ ነበር” አልኩ። “ታውቃለህ!?” አለኝ፤ “አንድ የመንግስት የበላይ ባለስልጣን ወይንም ወዳጁ፤ በማንኛውም ሰአት የኔ ቢዝነስን ሼር ሆልደር ልሁን ወይም ልግዛህ ካለኝ በደስታ እቀበላለሁ። ባይገርምህ እስካሁን ስንት የንግድ ድርጅቶች ቀያይሬአለሁ መሰለህ!” “ባክህ ተወኝ ብዙ አታሶራኝ እኔ ተመችቶኛል። ይልቁንስ የሚያሳዝኑኝ ድርጅታቸው ሲቀማ፤ እንደ አዲስ መጀሩ ታክቷቸው ነገር አለሙን እርግፍ አርገው የሚተዉት ሰዎች ናቸው።” “እኔ እንኳ በአዲስ መጀመር ምንም አይመስለኝም፤ ከንግዲህ እንዳትሰራ ካላሉኝ በስተቀር።” አለ ፈገግ ብሎ እየተመለከተኝ።

“አሁን ግልፅ ሆነልክ!?” ጠየቀኝ፤ ነገር ግን መልሴን ሳይጠብቅ ንግግሩን ቀጠለ፤ “ስለዚህ ህጉ ላጲስ አለው ያልኩህ ለዚህ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ወንጀል እንደ እኔ አይነቱን ልማታዊ ዜጋ በህግ አያስጠይቀውም፤ አያስቀጣውምም።” “ለነገሩ ባለስልጣናቱንም አያስጠይቅም፤ ከዋናዎቹ ጋር እስካልተቃረኑ ድረስ።” “እስኪ በየ እስር ቤቱ የታጐረውን ዜጋ አስብ!!!? እውን እንደሚባለው ወንጀል ፈፅሞ ይመስልካል!?” “የትኞቹ ጋዜጠኞች ናቸው ወደ እስር ተወርውረው የተረሱት!?” “ፖለቲከኞቹስ ቢሆኑ!? ሁሉም የሚታሰሩ ይመስልሃል!?” “ስንቱ ከስራ ተባሮ ቦዘኔ ደሓ ሁኖ የቀረው ስራውን በአግባቡ ስለማይሰራ ይመስልሃል!?”

“ስለዚህ እመነኝ፤ እኔ ለልማታዊው መንግስታችን የምመች ልማታዊ ዜጋ ሆኛለሁ።” “መንግስታችን እንደኔ አይነቶቹ ዜጐች ከሌሉ ለህልውናው ስለሚሰጋ ይንከባከበናል። ስለዚህ አትጨነቅ።” “በርግጥ ይህን እንዳጫወትኩህ ከሰሙ ነገ ወደ እስር ቤት እንደምጓዝ አትጠራጠር። ለነገሩ አንተ ካልነገርካቸው በስተቀር የዛሬው ጨዋታችንን አይሰሙትም። ምክንያቱም አይከታተሉኝማ፤ አውቃለሁ።” “እነርሱ የሚከታተሉህ ‘ልማታዊ ዜጋ’ ካልሆንክ ብቻ ነው።”አለና ቀና ብሎ እያየኝ “አሁን ገባህ!? መንግስታችን የሚያወጣቸው ህጐችና መመሪያዎች ከጐናቸው ላጲስ አሏቸው።” “በላጲሱ ማጥፋት የሚችለው ግን መንግስታችን ብቻ ነው።” “እንዲያጠፋልክ የምታዘው ደግሞ አንተ ነህ፤ ‘ልማታዊ ዜጋ’ በመሆን።” “ይሄው ነው ወዳጄ።” አለኝ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!

Comment

The post ልማታዊው ጓደኛዬ – ከዋስይሁን ተስፋዬ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

አስቂኙ የአቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ቃለ መጠይቅ! –ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

$
0
0

amsaluየኢሳት ራዲዮና ቴሌቪዥን (ነጋሪተ ወግና ምርዓየ ኩነት) ጋዜጠኞች ከሕዝባዊ ግንባር መሪ አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ጋር ያደረጉትን ቃለ መጠይቅ ተከታተልነው፡፡ ያው አስቀድሜ እንደገመትኩት በአሮጌው ድሪቶ ላይ አሮጌ ጨርቅ ድረታና እብለት ክህደት እንጅ የነበረውን አሮጌውንና ያላዋጣውን በመተው በአዲስና በተመከረ በተማረ ልብ አዲስ ሐሳብ አዲስ መንገድ ለመቀየስ አልተፈለገም፡፡ የሚጠበቀውና አስፈላጊው ግን ይሄኛው ነበር፡፡ ለነገሩ ከአንባገነን ሥርዓት ባለሥልጣናት ይሄ የሚጠበቅ አይደለም እንደነዚህ ዓይነት ሰዎች እንኳን በአንድ ሰው ዕድሜ ሽህ ዓመታት የመኖር ዕድል ቢሰጣቸው እንኳን እስከ መጨረሻዋ ደቂቃ ድረስ ሱሪያቸውን በአንገት ለማጥለቅ እንደታገሉ ያልፋሉ እንጅ አይ ሐሳቤ መንገዴ ይሄንን ያህል ዘመን ብታገልም ሊሠራ አልቻለም፡፡ ሊሠራ ያልቻለበትም የራሱ ምክንያት ችግር ስላለበት ሳይሆን አይቀርምና እስኪ ወይ ለሌላው ዕድሉን ልስጥ ወይ አስተሳሰቤን ቀየር ላድረገው አይሉም፡፡ ተፈጥሯቸው አይፈቅድላቸውምና ግትሮች ናቸው፡፡ ሰውየውን አላያቹህትም?  ጓደኞቹን ሰጥ ለበጥ አድርጎ እንቢ ያለውን አጥፍቶ ፈላጭ ቆራጭ ሆኖ ብቻውን ገኖ መግዛት በመቻሉ የሚነበብበትን የእርካታ ስሜት አልታያቹህትም? የተሳካላት የሞላላት ሀገር መሪ እንጅ በተወሳሰበ ችግር ውስጥ ያለች ከዕለት ወደ ዕለት እየተመሰቃቀለች የሕዝቧ ኑሮም እየከፋ ያለች ሀገር መሪ ይመስል ነበር?

እናም ከቃለ ምልልሱ አንድም እንኳን ፍሬ አላገኘሁበትም፡፡ እንዲህ ይባላል እንዲህ ይባላል ስለሚባሉ ነገሮች ተወራ እንጅ በፖለቲካዊ (በእምነተ አሥተዳደራዊ) ጉዳዮች ላይ ግብራዊ (ቴክኒካል) የሆኑ ጥያቄዎች ለምሳሌ በአሰብ ወደብ ዙሪያ ያለውና የመሳሰሉ ዋና ዋና ጉዳዮች ስላልተዳሰሱበት በግሌ ቅር ብሎኛል፡፡ ሲጀመር ቃለ መጠይቁ የቃለ መጠይቅ አሠራርናንና ሒደትን የተከተለ አይደለም፡፡ ጋዜጠኞቹ ትግርኛን ባለማወቃቸው ጥያቄዎችን መጠየቃቸውን እንጅ የጠየቁት ጥያቄ በአግባቡ ስለመመለሱና አለመመለሱ ማረጋገጥ እንዳይችሉ አድርጓል፡፡ ሰውየው ማውራት የምፈልገው በትግርኛ ነው ካሉ መብታቸው ነው ነገር ግን የሚመልሱትን ለጋዜጠኞቹ የሚተረጉም አስተርጓሚ በመሀል መኖር ነበረበት፡፡ ይሄ ባልሆነበት ሁኔታ እንዴት ቃለ ምልልሱን ለማድረግ እንደፈቀዱ አልገባኝም፡፡ አስተርጓሚ ከሌለም ጠያቂዎቹና ተጠያቂው በጋራ በሚያውቁት ቋንቋ መደረግ ነበረበት፡፡ ወደ ኋላ ላይ አቶ ኢሳይያስ ከትግርኛ ወደ እንግሊዝኛ በመሔዳቸው ለጋዜጠኞቹ ሰውየው የሚሉትን ነገር ምንነት ለመረዳት የተሻለ ዕድል የሰጣቸው ቢሆንም የተጠቀሙበት ግን አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም ጥያቄው ይጠየቃል ሰውየው የፈለገውን ሰዓት ያህል ወስዶ ሌላ ነገር ሲቀበጣጥር ቆይቶ ሲጨርስ ሌላ ጥያቄ ደሞ ይጠይቃሉ እንጅ ከጭብጥና ከነጥቡ ውጭ ሲወጣባቸው መመለስ፣ በአግባቡ ያልተመለሰውን እንዲመልስ ማድረግ፣ በዋሸባቸው ወይም በካዳቸው ባበለባቸው ጉዳዮች መሞገት የተባሉ የጋዜጠኛ ሥራዎች ሲሠሩ ባለማየቴ ከፍቶኛል፡፡ ኢሳት ኢሳትን እንጅ ኢቴቪን መሆን አልነበረበትን፡፡ በእርግጥ እነዚህ የኢሳት ጋዜጠኞች ከብቃት ማነስ ሳይሆን ከአቶ ኢሳይያስ ጋራ በገለጽኩት መልኩ ቃለ መጠይቅ ማድረግ እንደ ሌሎቹ ሁሉ እነሱንም እንዳይመለሱ አድርጎ ወኅኒ ሊያስወርዳቸውም ይችላልና ይሄንን ከመፍራት ሳያደርጉት ቀርተው ከሆነ ልንረዳላቸው ይገባል፡፡ አስቀድሞ እንዲህ ዓይነት ሥጋት ከነበራቸው ደግሞ ቃለመጠይቁን ማድረጉ አስፈላጊ አልነበረም፡፡

አንዴ ብቻ አቶ ኢሳይያስ 90ሽህ የደርግ ወታደሮችና ባለሥልጣናት ከባሕረምድር ተሸንፈው በሚወጡበት ወቅት “እንኳን የበቀል እርምጃ ስድብ እንኳን የተናገራቸው አንድ ሰው እንኳን የለም” በማለት የሰውየውን የውሸታምነት ደረጃ የሚያሳይ አስቂኝ ቃል በተናገሩ ጊዜ ፋሲል ምንም እንኳን ሰውየው ተናግረው ጨርሰው ሌላ ጥያቄ ለመቀበል በተዘጋጁበት ሰዓት ቢሆንም “እዚህ ላይ ይቅርታ ላቋርጥዎት” በማለት እነዚህ አቶ ኢሳይያስ 90 ሽህ ናቸው ያሏቸው የደርግ ወታደሮችና ባለሥልጣናት ጥርሳቸውን ሳይቀር እንዲወልቅ እንደተደረገ የእጅ ሰዓት የአንገት ሀብልና ሌሎች ንብረቶች ሁሉ እንደተዘረፉ በታሪክ እንደሰማ አሁን እሳቸው ያሉት ደግሞ ከዚህጋር እንደተለየበት ጠይቋቸው ነበር፡፡ ምንም እንኳን አቶ ኢሳይያስ ለዚህ ጥያቄ ምን እንደመለሱ ኢሳት ባያስደምጠንም ቅሉ፡፡ ለመሆኑ የዚህን ጥያቄ መልስ እንዳንሰማው የተደረገው ለምንድን ነው?

አቶ ኢሳይያስ የገረሙኝ ነገር ቢኖር ፖለቲካዊ ጉዳዮችንስ እሽ መደበቅ የሚፈልጉት ጉዳይ ስለሚኖር ለመሸሽ ሌላ ሌላ ነገር ቀበጣጥረው አለፉ እንበል እሳቸው እኮ ቢናገሩት አድማጩን ምንም የማይጠቅመውንና የሚያውቀውን ጉዳይ ሁሉ እኮ ነበር ሊናገሩ ያልቻሉት፡፡ ለምሳሌ ስለ ራሳቸው ስለ ልጆቻቸው ተጠየቁና ሲመልሱ ይሄም ቁም ነገር ሆኖባቸው ልጆቻቸው ማን ማን እንደሚባሉና ስንት እንደሆኑ ምን እንደተማሩ አንድም ነገር ሳይናገሩ ተፈላሰፍኩ አሉና “ዘለው የባለ ሥልጣን ልጆች ስለሆኑ ከሌላው በተለየ ሊታዩ አይገባም እነሱም ሰው ናቸው ሁለት ዐይኖች እንጅ አራት ዐይኖች የላቸውም ሁለት ጆሮዎች እንጅ አራት ጆሮዎች የላቸውም ሁለት እግር እንጅ ሁለት እጅ እንጅ አንድ አፍንጫ እንጅ አንድ ምንትስ ሁለት ቅብርጥስ” እያሉ በመዛዛት ስንት ነገር ሊሠራበት የሚችለውን ወርቃማ ጊዜ እንዲያው በከንቱ አባከኑብን፡፡ ከሰው ልጅ ከተወለዱ ሁለት አንድ እያሉ የዘረዘሯቸውን የሰውነት አካላት እንደሚይዙ ማን ያጣዋል ብለው ነው አቶ ኢሳይያስ? መጀመሪያ እነማን እንደሆኑ መች አስተዋወቁንና? ስለነሱ ልናወራ የምንችለው መጀመሪያ ልጆች እንዳሏቸው ሲያሳውቁን አልነበረም እንዴ? ያሉት ነገር እውነት በሆነ በእውነት ከፍልስፍና በቆጠርኩልዎት ነበር እርስዎንም ለሕዝብ እንደሚያስብ ቅን አሳቢ ቡቡ መሪ በቆጠርኩዎት ነበር፡፡ አቶ ኢሳይያስ እንዲያው ግን ሰው ይታዘበኛል የሚባል ኅሊናም የለዎት? አሁን ማን ይሙትና እርስዎን ጨምሮ ልጆችዎ የእርስዎ ልጆች ኑሮ ከተራው ዜጋ ኑሮ ምንም ያልተለየ ነው? እርስዎና የእርስዎ ልጆች አብዛኛውን ጊዜ የሚበላውን አጥቶ በቀን አንዴ እንደሚበላው ባስ ሲልም ጦም እንደሚያድረው እንደአብዛኛው የገጠር ሕዝብዎና እንደከፊሉ የከተማ ሕዝብዎ ጦም አድራቹህ ወይም በቀን አንዴ ብቻ ተመግባቹህ ታውቃላቹህ? የምትቀይሩት ልብስ አጥታቹህ በአንድ ልብስ ላይ ተጣብቃቹህ ታውቃላቹህ? መኝታቹህን ትኋን ቁንጫና ቅማል ይዘልበታል? ባለው ከፍተኛ የውኃ ችግር እንደሌላው ሁሉ ልብሶቻቹህ ሳይታጠቡ ንጽሕናቹህ ሳይጠበቅ በክታቹህ ትሰነብታላቹህ? የማይመስል ነገር እየቀባጠሩ ሲወሸክቱ ምን ያህል ግብዝና አስመሳይ አታላይ መሆንዎ ነው ቁልጭ ብሎ የታየኝ፡፡

የጥያቄዎችን ጭብጥና ነጥብ ሳይጠብቁ የሰውነት አካላትን ሁሉ አንድ ሁለት እያሉ እርባና የሌለውን ዝባዝንኬና የባጥ የቆጡን ወሬ እየቀበጣጠሩ ረጅም ሰዓት ማውራት ችሎታና ብቃት መስሎዎት ነው አቶ ኢሳይያስ? ለዛ ነው እንዴ “በዚህ ጉዳይ ላይ ለሰዓታት ላወራ እችላለሁ!” ሲሉ ደረትዎን ነፍተው የተናገሩት? አየ አቶ ኢሳይያስ! እንደ ማን የሆኑ መስሎዎት ነው? እንደ ኩባው ፊደል ካስትሮ? ነው ወይስ እንደ ሊቢያው ጋዳፊ? እንዲህ ጊዜ ወርቅ በሆነበት ከወርቅም አልማዝ ከአልማዝም ዩራኒየም በሆነበት ዘመን በዝባዝንኬ ወሬ እርስዎም ሥራ ፈተው እኛንም ቁምነገር ያወራሉ መስሎን ሥራ አስፈትተው ይሆናል ብለው ነው? ነው ወይስ “ጊዜ ወርቅ ነው” የሚለው ብሂል ገና እርስዎ ላይ አልደረሰም? አዎ በሥራዎ በአስተሳሰብዎ ሁሉ እያየነው አይደል? አሁን ሌላ ጊዜ አቶ ኢሳይያስ ቃለ መጠይቅ አላቸው ቢባል ማን ነው ቁጭ ብሎ የሚሰማልዎት? አየ አቶ ኢሳይያስ! ለሌላው ጊዜ ግን ሲጠየቁ በነጥቡ ላይ ብቻ አተኩረው ከጭብጥ ሳይወጡ ጥያቄውን መመለስ ነው እንጅ ያልተጠየቁትን የሰውነት አካላት በመዘርዘር የሰው ውድ ጊዜ አያባክኑ እሽ? መመለስ የማይፈልጉት ጥያቄ ካጋጠመዎት ደግሞ እንደሌሎቹ መዝለል ነው እንጅ የማይረባ ዝባዝንኬ መቀበጣጠር ያስገምትዎታል፡፡

አቶ ኢሳይያስ በጣም አስገራሚ ሰው ነዎት፡፡ ፍልስፍናው እንደሱ አይደለም፡፡ ቅዠት በሆነና የትም ቦታ ባልታየ ሊታይ ሊተገበር ባልቻለ የኮሚውኒዝምና (መደባዊ ያልሆነ ሥርዓተ ማኅበር) የሶሻሊዝም (የኅብረተሰባዊነት) ፍንስፍና እየዳከሩ ጊዜዎን በከንቱ ባያቃጥሉ ሕዝቡንም ባያደክሙ ባያንገላቱት መልካም ነው፡፡ ምክንያቱም ይሄ ፍልስፍና ሲበዛ ተምኔታዊ (Ideal) በመሆኑና ማንም ሀገር በትክክል ሊተገብረው ስላልቻለ ሊተገበርም ስለማይቻል፡፡ ሲሰሙት ደስ ይላል አማላይም ነው ተግባራዊ ማድረግ ግን ፈጽሞ የሚቻል አይደለም፡፡ እዚህ ላይ ትንሽ የጭንቅላት እጥበት (brain wash) ላደርግዎት እፈልጋለሁ፡፡ ይሄውልዎት አቶ ኢሳይያስ እያንዳንዱ ሰው የልፋቱን ያህል ማግኘት ካልቻለና ጠንካራውም ደካማውም ምሁሩም መሀይሙም እኩልና ተመሳሳይ የኑሮ ደረጃ እንዲኖረው ከተደረገ ውጤቱ ሰውን ከአቅም በታች እንዲሠራ እንዲለግም ያደርጉታል በዚህም ሀገር ትጎዳለች እንጅ እንዲተጋ፣ አቅሙን አሟጦ እንዲፈጋ፣ እራሱን በሥራ እንዲጠምድ፣ ለጥራት ትኩረት እንዲሰጥ ሊያደርጉት አይችሉም ንግድን ጨምሮ ሌሎች እንቅስቃሴዎች ሁሉ አይነቃቁም፣ ኑሮ ፉክክር የሌለበትና አሰልች ይሆናል ፈጠራ ግኝትና ፍልሰፋን የመሰሉ የንቁ ጭንቅላት ፍሬዎችማ ጨርሶ የሚታሰቡ አይሆንም፡፡ ሰው አዳዲስ ነገር ሊፈጥር ሊያገኝ ሊፈለስፍ የሚችለው የሚበረታታው የድካሙን የልፋቱን የጥረቱን ያህል ሲከፈለው ዕውቅናና አክብሮት ሲቸረው እንጅ ያንን ያህል ደክሞ ለፍቶ ጥሮና ግሮ ከተራው ዜጋ ጋር በተመሳሳይ የኑሮ ደረጃ እንዲኖር ሲደረግ አይደለም፡፡ ይሄ የሥራ መነቃቃት ስሜትን ይገላል፡፡ ለብርቱው ለታታሪው ለጠንካራው የየጥረቱን ያህል ዳጎስ ዳጎስ ያለ ክፍያ ሲከፈለው ግን መነቃቃት ይፈጠራል፡፡

አንድ ቀላል ምሳሌ ልስጥዎት አቶ ኢሳይያስ፡- በአንድ ክፍል ውስጥ ተማሪዎች ብቃታቸውና ችሎታቸው የተለያየ ሆኖ እያለ እኩል ነጥብ ልስጥ ይላሉ እንዴ? ሁሉም ተማሪዎች እኩል የመቀበልና የመረዳት አቅም ችሎታ ሊኖራቸው አይችልምና ወይም አንደኛው ከሌላኛው ሊጎብዝና ሊሰንፍ ይችላልና እኩል ነጥብ ልንሰጥ አንችልም አይገባምም ካደረግነውም አሠራራችን ፍትሐዊና አመክንዮአዊ አይሆንም፡፡ የተፈጥሮ ጉዳይ ነውና ሁሉንም እኩል ማጎበዝ እኩል እንዲያስቡ ማድረግም አይቻልም፡፡ ልናደርግ የምንችለው ሁኔታዎችን በማመቻቸትና በመርዳት የሚሰንፍ ሰው እንዳይኖር ምርጥ ብቃቱን ችሎታውን እንዲጠቀም ማድረግ፡፡ እንዲህ አድርገን ከረዳናቸው በኋላ ችሎታቸው ብቃታቸው በፈቀደላቸው መጠን የሚያመጡትን ውጤት ግን የየችሎታቸውንና ውጤታቸውን ያህል ነው ሊሆን የሚገባው፡፡ ይሄ ካልሆነና ለሁሉም እኩል ነጥብ የሚሰጥ ከሆነ ግን የሚጎብዝ ተማሪ ሊወጣ አይችልም፡፡ ምን አለፋውና? በሥራም ዘርፍ ያለው ነገር እንዲሁ ነው፡፡ ስለሆነም ጠንክሮ በርትቶ የሠራ ሀብታም የሚሆንበት የተሰጠውን ዕድልና ድጋፍ መጠቀም ሳይችል ቀርቶ የወደቀው ደግሞ ደህይቶ በድህነት የሚቀጣበት ሁኔታ ክፍት መሆን አለበት፡፡ ባለፀጋው በድካሙ በጥረቱ በልፋቱ አግኝቷልና የድካም ፍሬውንም እንዲበላ ሊፈቀድለት ይገባል፡፡ ሰው የሚደኸየው በስንፍናው ብቻ አይደለምና ባለጸጋው በሰብአዊነት በራሱ ፈቃድ ድሆችን መርዳት ከፈለገ ግን የፈቀደውን ያህል ያለውን ማካፈል መብቱ ነው፡፡ የሞራል (የቅስም) ግዴታም አለበት፡፡ በግድ ግን ያለህን አምጣ ከሌላው የተለየ የላቀ ኑሮ ልትኖር አትችልም ሊባል አይገባም፡፡ በዚህ ዓይነት አሥተዳደር ሀገር ልትገነባ ዜጎች ሊለወጡ አይችሉም፡፡

የሀገራት መሪዎች ሊጠነቀቁ የሚገባው ነገር ቢኖር ለሁሉም ዜጋ ሠርቶ ሊለወጥ ሊበለጽግ የሚችልበት እኩል ዕድል የመኖሩን ጉዳይና ሕግ ከፈቀደው መንገድ ውጪ ሊበለጸግ የሚቻልበትን ሙስናን የመሰለ አግባብ ያልሆነና ሕገ ወጥ አሠራር ኖሮ ዜጎች ሠርተው መለወጥ የሚችሉበትን ዕድል አጥተው ጥቂቶች ወንጀለኞች ብቻ ደግሞ የሚበለጽጉበት ሁኔታ እንዳይፈጠር እንጅ በነጻና ፍትሐዊ ፉክክር የጠነከሩት የበረቱት ሠርተው ማግኘት መለወጥ የሚችሉት ዜጎች መኖራቸው አይደደለም ሊያሳስባቸው የሚገባው፡፡ ይሄማ ሥጋት ነው ሊሆን የሚችለው የአንባ ገነን መሪዎች ሥጋት፡፡ በበረቱ በበለጸጉ በነቁ በበቁ ሰዎች እንዋጣለን ጥቅማችን ይጎዳል ሥልጣናችንን ሁሉ ልናጣ እንችላለን የሚል የሀገርን ጥቅም ሳይሆን የግል ጥቅማቸውን ማዕከል ያደረገ ሥጋት፡፡ ሲመስለኝ የእርስዎም ሥጋት ይሔው ነው ምክንያቱም ከላይ እንደገለጽኩት እርስዎ የተናገሩትን እርስዎም ሆኑ ልጆችዎ አትኖሩትምና ነው፡፡ ጉርድ ሸሚዝና ክፍት ጫማ አድርገው መታየትዎ ወደ ኋላ ላይ ተስቶዎት እውነቷን እንደተናገሩት ቀለል ያለ የኑሮ ዘይቤ ስለሚወዱ እንጅ መግቢያዎ ላይ ለማወናበድ ይታሰብልኛል ብለው እንደገመቱትና እንደተናገሩት ከተራው ሕዝብ የተለየ ኑሮ እንዲኖርዎት የማይፈልጉ ስለሆኑ አይደለም፡፡ ባሰኘዎት ጊዜና ቦታ ደግሞ እንዴት እንደሚዘንጡ በሚገባ እናውቃለንና፡፡ በእርግጥ አንዳንድ የዋሀንን ሊያታልሉ ይችሉ ይሆናል የሆነ ሆኖ ግን እውነት ያልሆነና የማስመሰል ነገር መሠረታዊ የሆነ ለውጥ አያመጣምና እንዲህ ዓይነቱን ነገር ቁም ነገሬ ብለው ባይይዙት መልካም ነው፡፡ እርስዎንም ማንንም አይጠቅምምና፡፡

በተመሳሳይ ስለ የትጥቅ ትግል ለማድረግ እናንተጋ ስላሉት የተቃውሞ ኃይሎች “ሸአቢያ አንድ እንዳይሆኑ ያደርጋል፣ በዘር ወይም በብሔር እየከፋፈለ በማደራጀት የተለያየ ዓላማ ያላቸውን የተለያዩ ብሔር ተኮር የፖለቲካ ድርጅቶችን ይፈጥራል ይባላልና ለዚህ ምላሽዎ ምንድን ነው?” ተብለው ለተጠየቁት በመቀበጣጠር “ኦነግን፣ ኢሕአፓን፣ ምንትስን እያሉ እኛ ከመመሥረታችን በፊት የተመሠረቱ በመሆናቸው እኛ ልናደራጃቸው አንችልም” አሉ ታደራጃላቹህ የተባላቹህት መቸ እነሱን ሆነና? በደንብ ካላዳመጡ ጥያቄው እንዲብራራልዎት መጠየቅ ነው እነማንን ማለትህ ነው ቢሉ ይዘረዘርልዎት ነበር እነሱንስ ቢሆን እንዳይግባቡና አንድነት እንዳይፈጥሩ እንደሚያደርጉ የማናውቅ ይመስልዎታል? አዳዲሶቹን በሀገሪቱ ያለው የወያኔ የዘር ፖለቲካ የፈጠራቸው እንጅ እኛ አልፈጠርናቸውም አሉ “ለማያውቅሽ ታጠኝ” አለ ያገሬ ሰው እነ መለስ ሕገመንግሥቱን ሲያሳዩኝ የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘር የሚከፋፍልና የማይጠቅም ነው ብለው ወያኔን የመከሩ ሰው ከሆኑ በወያኔ የዘር ፖለቲካ ተሳስተው በሀገርዎ የተደራጁ ወገኖችን መክረውና እንደማይጠቅም አስረድተው በአንድ እንዲደራጁ ማድረግ ምን ነው ተሳነውትሳ ታዲያ አቶ ኢሳይያስ?

እኔማ የሚጠየቁት ሌላ የሚመልሱት ሌላ ማሞ ሌላ መታወቂያው ሌላ ፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ አራንባና ቆቦ እየሆነ ሲያስቸግረኝ ይቅርታ ይደረግልኝና ሰውየው ጤነኛ መሆናቸውን ሁሉ ለመጠራጠር ነው የተገደድኩት፡፡ ዝም ብሎ ይቀዳል ሰውየው እውነት ተናገረ ውሸት የሚለውን ለጊዜው እንተወውና እንደ ፖለቲከኛ እንኳን ምን ብል ይታመንልኛል? ምንስ ብል አይታመንልኝም? የሚለውን ነገር ጨርሶ መለየት የሚችል ሰው ሆኖ አላገኘሁትም፡፡ ጤነኛ ሰው እኮ ሲጠይቁት ምን እንደጠየቁት አውቆ ተረድቶ የተጠየቀውን በአግባቡ ሲመልስ እንጅ የተጠየቀውን ትቶ ጨርሶ የማይገናኝ ነገር ከቀበጣጠረ እንዴት ነው ጤነኛ ነው ልንል የምንችለው? ባጠቃላይ ሰውየው አውርቶ የሄደው ሊያወራው ሲዘጋጅበት የሰነበተውንና የሸመደደውን ነገር ነው አውርቶ የሄደው ጥያቄ የተባሉት ባይሰነዘሩና ቪዲዮ ካሜራ (መቅረጸ ትዕይንት) ደቅነው ቢተውለት ራሱ ይሄንኑ ራሱን አንዳችም ሳይቀንስ ሳይጨምር ሊያወራላቸው ይችል ነበር፡፡

ሲያወራው የነበረው በጠቅላላ ሐሰት ነበር፡፡ ምን እንደሚዋሽም አላወቀም ለምሳሌ እነዚያ 90 ሽህ የተባሉ የደርግ ወታደሮችና ባለሥልጣናት ሁሉም ባይሆኑ በአብዛኛው በሕይዎት ባሉበትና የተፈጸመባቸውን ግፍ በሚገባ ሊናገሩ ሊመሰክሩ ሊያረጋግጡ በሚችሉበት ሁኔታ ሽምጥጥ አድርጎ ክዶ “እንኳን የበቀል እርምጃ ስድብ እንኳን የተናገራቸው አንድ ሰው የለም” ባለበት ሁኔታ ሰውየው ምን እንደሚያስተባብል ምን እንደማያስተባብል ለይቶ ያውቃል ማለት እንዴት ነው የሚቻለው? አቶ ኢሳይያስ ያ የሠሩት ግፍ ከባድነት ታወቃቸው እንዴ? ነው ወይስ ካደረሱባቸውም ግፍ በላይ ሳይፈጇቸው በመልቀቃቸው ቆጫቸው?

ለነገሩ ሰውየው ይሄ ጠፍቶት አይመስለኝም ሰውየው ከገመትኩት በላይ የተዋጣለት አሽሙረኛ ሆኖ ነው ያገኘሁት፡፡ አቶ ኢሳይያስ በወቅቱ 90 ሽህ ናቸው ባሏቸው የደርግ ወታደሮችና ባለሥልጣናት  ላይ ምን ምን ዓይነት ግፍ እንደተፈጸመባቸው በምን መልኩ ሰብአዊ ክብራቸው ተዋርዶና ንብረታቸው ተዘርፎ የወርቅ ጌጣጌጥ እንደ ቀለበትና ሀብል ደብቃቹሀል እየተባሉ እያስጎነበሱ ፍንጢጣቸው ሳይቀር እየተፈተሸ ከለበሱት ልብስ አቅም እንኳን እያስወለቁ ድሪቶ እያለበሱ ወይም እርቃናቸውን እየሆኑ እንዲወጡ እንደተደረጉ አቶ ኢሳይያስ አትተውት ወይም ሳያውቁ ቀርተው አይደለም፡፡ ነገር ግን የደርግ ወታደሮችና ባለሥልጣናት የነበሩት በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ሆነው አሁንም ድረስ በተቃውሞው ጎራ ተሰልፈው ሀገራቸውን ለማገልገል በሚያደርጉት ጥረት ሸአቢያ ጥቅሙ እየተጎዳበት ማንነቱ እየተጋለጠበትና በ1990ዓ.ም. ላይ በተደረገው ጦርነትም ጉልህ ሚና መጫወታቸው እነዚህን ወገኖች በሕይዎታቸው የማይረሱትን ክፉ የሕይዎት አጋጣሚ እንዲያስታውሱት አድረገው አቁስለው ሲያበቁ እንደገና ደሞ ያኔ ከተፈጸመባቸው ግፍ በላይ የተፈጸመባቸውን ግፍ ፈጽሞ እንዳልተፈጸመባቸው ተደርጎ ተሸምጥጦ በመካዱ እንደገና እንዲቆስሉ እንዲያሩ እንዲበግኑ ማድረግ ፈልጎ ነው ሰውየው ሀገር ያወቀውን ፀሐይ የሞቀውን የአደባባይ ምሥጢር ሸምጥጦ ለመካድ የሞከረው፡፡

እናም ብቻ በእነዚህ በእነዚህ ምክንያቶች ይሄ ቃለ መጠይቅ እርባና ቢስ የሚነሣ ነገር አንድ እንኳ የሌለው ነው የሆነብኝ፡፡ ነገር ግን እንዲያው አንዳንድ የገረሙኝንና የሰውየውን የዋህነት አጉልተው ያሳዩኝን አንዳንድ ነገሮች ሰውየውንም ሀገራችንንም ሕዝባችንንም እጅግ የሚጎዱ ሆነው ስላገኘኋቸው በእነሱ ጉዳዮች ላይ ማውራት ግድ ብሎኛል፡፡

አንደኛው አቶ ኢሳይያስ ፈርጠም ብለው ሲናገሩ ምን አሉ? “የሁለቱም ሀገሮች ግንኙነት 1997 (1989ዓም.) በፊት ወደ ነበረው ሰላማዊ ግንኙነት መመለስ አለበት” አሉ፡፡ ይህች አነጋገር እንዲህ ቀላል አነጋገር እንዳትመስላቹህ፡፡ አቶ ኢሳይያስ እንዲህ ሲሉ ምን ማለታቸው እንደሆነ ለብዙዎቻችን ግልጽ እንዳልሆነ እገምታለሁ፡፡ አቶ ኢሳይያስ እንዲህ ሲሉ ምን ማለታቸው ነው? እንደምታስታውሱት ወያኔና ሸአቢያ ግፍን የሚመለከተው የመድኃኔዓለም እጅ ገብቶበት ግንኙነታቸው ሻክሮ ከመጣላታቸው በፊት ሸአቢያ በሀገራችን የኢኮኖሚ (የምጣኔ ሀብት) እንቅስቃሴ ከፍተኛ ጫና ይፈጥር ነበር፡፡ አንድ ምሳሌ ብሰጥ ኤርትራ አንድ እንኳን የቡና ችግኝ የማይገኝባት ሆና እያለ በዓለም ካሉ ታዋቂ ቡና ላኪ ሀገራት ውስጥ አንዷ ሆና የተመዘገበችበት ሁኔታ ተፈጥሮ ነበር፡፡ ቡናችንን ብቻ ይደለም እንደ ሰሊጥና ጥጥም የመሳሰሉ የግብርና ምርቶቻችንንም እንጅ፡፡ በዚያ ወቅት ሸአቢያ ያለ አንዳች ከልካይ በሀገራች ገበያ ላይ እንደፈለገ እየዋኘ ምርቶችን እየጫነ እየወሰደ ነበር ለውጭ ገበያ ያቀርብ የነበረው፡፡ አቶ ኢሳይያስ 1989ዓም. በፊት ወደ ነበረው ግንኙነት መመለስ አለበት ሲሉ አሁንም እንደያኔው ገብቸ የምዘርፍበት ሁኔታ መፈጠር አለበት ማለታቸው ነው፡፡ ለጦርነቱ መፈጠር መንስኤ የሆነውም ይሄው ነው ወያኔም በመንቃቱና ሸአቢያ የሚያገኘውን ጥቅም በንግድ ድርጅቶቹ በኩል ለራሱ ሊበላ ስለፈለገና ሸአቢያን በመከልከሉ በተፈጠረው ውዝግብ ሸአቢያ እነዚህንና ሌሎች ምርቶችንም ከሀገራችን እየዘረፈ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የማይችልበት ሁኔታ መፈጠሩ ነው የጦርነቱ መንስኤ፡፡ ባድመ ሰበብ እንጅ ትክክለኛው መንስኤ እሱ አልነበረም፡፡ እናም አቶ ኢሳይያስ ያ ወርቃማ ዘመናቸው ዛሬም ድረስ በዐይናቸው እንደዞረ አለ ደግመው ሊያገኙትም እጅግ ይመኛሉ ይቋምጣሉም፡፡

እኔ ከዚህ ቃለ መጠይቅ የተረዳሁት ነገር ቢኖር ሸአቢያ ከሚገመተው በላይ አደገኛ የሆነ የጥገኝነት ተፈጥሮና አስተሳሰብ እንዳለበት ነው፡፡ ከዚህ የተነሣ ነው አቶ ኢሳይያስ “የኛ ፍላጎት የነበረው ከኢትዮጵያ ጋር በአንድ ገንዘብ፣ በአንድ የቁጥጥር (monitory) እና የመንግሥት ገቢ (fiscal) መመሪያ (policy) እንድንተዳደር ነበር” አሉ፡፡ ይታያቹህ! አቶ ኢሳይያስ ለመሆኑ ተገንጥለናል ራሳችንን የቻልን ሉዓላዊ ሀገር ሆነናል ካሉ በኋላ እንዴትና ለምንድን ነው እሱ በአንድ ገንዘብ፣ በአንድ የቁጥጥር (monitory) እና የባጀት (fiscal) መመሪያ (policy) እንድንተዳደር የተፈለገው? በጣም የሚገርም እኮነው! እንደ አቶ ኢሳይያስ ያለ የድንጋይ ዳቦ ዘመን ብልጥ ሰው አጋጥሟቹህ ያውቃል? ለመሆኑ እንዲህ ዓይነት ግንኙነት ተጎዳኝተን ስናበቃ ሀገራችንን ማን እንድንላት ነበር ያሰቡት አቶ ኢሳይያስ? የተባበረችው ኢትዮጵያ ነው ወይስ ሌላ ስም ነበረዎት? ለካ የአፍሪካ ሲንጋፖርን የመፍጠር ሕልምዎን እውን ሊያደርጉት ያሰቡት በሀገራችን ሀብት ኖሯል? ባይሆንማ ኖሮ እነሆ ሲንጋፖር ሲሆኑ እናይዎት አልነበር! ለነገሩ እርስዎ ምን ያድርጉ ይሄንን እንዲያስቡ ያስገደደዎት ባሕረ ምድርን ከገነጠሉ በኋላ ባሕረ ምድርን እንደሀገር ህልውናዋን ለማስቀጠል ብሎም ለእድገት ብልጽግና ለማብቃት የሚያበቃ የተፈጥሮ ሀብት አልባ ሀገር ሆነችብዎት አይደል? ማጣፊያው አጠረብዎት አይደል? ሲጨንቅዎት ምን ያድርጉ? ያለዎት አማራጭ ሀገራችንን እየቦጠቦጡ የአፍሪካን ሲንጋፖር ማለም ነው፡፡

“የምን ዐይነ ደረቅ” የሚባለው ነገር ነው የሆነብን፡፡ አዩት አይደል የእርስዎን (የሕዝባዊ ግንባርን) ስሕተት? ሀገር እንደ ገበሬ ጓሮ ለብቻየ ተብሎ የሚፈጠር ነገር አለመሆኑን ተረዱት አይደል? ሀገር ሲታሰብ ብዙ ነገር ያስፈልጋል፡፡ ይሄንን ሁሉ ነገር ቀድሞ ለማየት ለመገመት የሚችል ጭንቅላት ስላልነበረዎት ይህ የገጠመዎት ችግር በፊት አልታየዎትም ነበር፡፡ በእርስዎ እውቀትና እምነት አንድ የሆነ መሬትን ቆርሶ ወይም ገንጥሎ መውሰድ ከተቻለ ሀገር የሚሆን ይመስልዎት ነበር፡፡ የሚያሳዝነኝ ነገር እንዲህ እንደእርስዎ ባሉ ሰዎች የሕዝብ ዕጣ ፋንታ መወሰኑ ብቻ ሳይሆን ድርጊታቹህ የተሳሳተ እንደነበር ብታውቁም ተሳሳቱ ላለመባል ብቻ አምናቹህ አለመቀበላቹህና ለመታረም ባለመፈለግ ሕዝብን ተጨማሪ ዋጋ እንዲከፍል ማድረጋቹህ ነው፡፡ ስሕተትን ለመሸፈን መፍትሔ አድርጋቹህ ለመውሰድ የምትፈልጉት ጉዳይ ደግሞ ነገሩን ይባስ ከድጡ ወደ ማጡ የሚወስድ መሆኑ ነው ሌላው የሚገርመው ነገር፡፡ አሁንም ይህን መፍትሔ አድርጋቹህ ያያቹህትን ነገር ለዘለቄታው ማርድረግ ይቻላል ወይ? ብላቹህ ለማሰብ አለመቻላቹህ አሁንም ደካማ የማሰብ ችሎታቹህን የሚያሳይ ነው፡፡ አቶ ኢሳይያስ ፈጽሞ የፖለቲከኛ ጭንቅላት የለዎትም ሌላ ሊሠሩ የሚችሉት ነገር ካለ ትተውት ቢሄዱ መልካም ነው፡፡ እንዴ! እርስዎና ወያኔ የምትገርሙኝ ነገር ቢኖር እናንተ ያልቻላቹህበት እንደሆነ በእናንተ ስሕተቶች እኛ መሰቃየት አለብን እንዴ? ምናለ ሐፍረት ቢሰማቹህ? ምን ዓይነት ሰብእና ቢኖራቹህ ነው ሐፍረት የሚባል ነገር ጨርሶ ሊሰማቹህ የማይችለው? ለማንኛውም ሲያምርዎት ይቅር እርስዎና ቢጤዎችዎ ከድንቁርና ቅዠታቹህ ጋር ገሀነም ትወርዳላቹህ እንጅ ኢትዮጵያን በመቦጥቦጥ ሲንጋፖርን መሆን አይቻልም፡፡

ሌላው ደግሞ አቶ ኢሳይያስ ምን አሉ? “እኔ ስለ 3ሽህ ወይም ከዚያ በላይ ዓመታት ስላለው ታሪክ ማውራት አልፈልግም ማውራት የምፈልገው ከ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ወዲህ ያለውን ነው፡፡ ብዙ ጊዜ 20ኛው መቶ ክ/ዘ ታሪክ የአፍሪካ ሀገሮች ታሪክ ብለን ስንል የ 19ኛው መቶ ክ/ዘ መጨረሻ ታሪክ ማለታችን ነው፡፡ ምክንያቱም የቅኝ ግዛት ድንበር የሚባለው ነገር የሚመጣው ያኔ ነው፡፡ ከዚያ ውጭ ግን የአጋንንት ሳጥን (Pandora’s box) ምናልባት 19ኛው ወይም 18ኛው መቶ ክ/ዘ ቅኝ ግዛት ከመምጣቱ በፊት ይሄ አካባቢ ምን ይመስል ነበር? ብሎ መነጋገር ይቻል ይሆናል ይሄ ግን ሌላ ርእስ ነው እኛ አሁን ያለንበት ከአፍሪካ በቅኝ ግዛት መከፋፈል በኋላ የተፈጠረ ስለሆነ የኛ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው” በማለት ስለ እሳቸው እኔ ያፈርኩላቸውን ነገር ተናገሩ፡፡ አቶ ኢሳይያስ በእርስዎ ቤት መሳደብዎ ነው አይደል?

አቶ ኢሳይያስ ይሄንን የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን አዋጅ እየደጋገሙ የሚያነሡበት ምክንያት ቅኝ ገዣቸው ባሕረ ምርድ የሚለውን ኢትዮጵያን ሰሜናዊ ክፍል በኃይል ቆርጠው ስም ቀይረው ኤርትራ በማለት አዲስ ባወጡላት ስም የሚጠሯት ሀገራቸው ህልውና ከመቸ እንደሚጀምርና በአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአፍሪካ ኅብረት) አዋጅ መሠረትም የሀገር ህልውና እንደሚኖራት ለመሟገት ነው፡፡ ወደዚህ ዝርዝር ከመግባቴ በፊት ግን አቶ ኢሳይያስ የግሪኮችን ተረት (myth) አውቃለሁ ለማለት የአጋንንት ሳጥን (Pandora’s Box) “ላስተካክልላቸውና የፓንዶራ የአጋንንት ሳጥን ነው የሚባለው” ስለሱ ጥቂት ልበል፡፡ ይገርማል አቶ ኢሳይያስ ቅድመ 19ኛው መቶ ክ/ዘ ያለውን ታሪካችንን በፓንዶራ የአጋንንት ሳጥን (Pandora’s Box) መስለውታል፡፡ ይሄ ሰውየው ለሀገራችን ታሪክ ያላቸውን ከባድና ጤነኛ ያልሆነ ጥላቻ ያሳያል፡፡ ለመሆኑ የአጋንንት ሳጥን መባል ካለበት መባል ያለበት የትኛው ዘመን ነው አቶ ኢሳይያስ? እንዲያው ምን ዓይነት ጭንቅላት ቢኖርዎ እንዴትስ ቢያስቡ ነው ከነጻነቱ የአገርዎ ባለቤት ከነበሩበት ሕዝቡ በነጻነት የሀገሩ ባለቤት ሆኖ ይኖር የነበረበት ዘመን የአጋንንት ሳጥን ሆኖ በቅኝ ገዥ ተጠፍንጎ በገዛ ሀገሩ ባዕድ ሆኖ እንደ መገልገያ ዕቃ ተቆጥሮ በባርነት በግዞት በጭቆና የኖረበት ደግኖ የመላእክት ሳጥን የሚሆንበት በምን ሒሳብ በምን መመዘኛ ነው አቶ ኢሳይያስ? ግን ጤነኛ ነዎት ለመሆኑ?

አቶ ኢሳይያስን ልጠይቅ የምሻው ነገር ፍጹም እንከን ወይም የእርስ በእርስ ግጭት የሌለበት በተለይ ደግሞ እኛን በመሰለ የረጅም ዘመን ታሪክ ባላቸው ሀገራት ምንም ኮሽታ ያልነበረበት ሀገር አንድ እንኳን ሊጠቅሱልኝ ይችላሉ? ከእነዚህ ሀገራት ውስጥም በአንፃራዊ መልኩ ሲታይ ከእኛ የተሻለ ሰብአዊነት የነበረበት ሀገር አንድ እንኳን ሊጠቅሱልኝ ይችላሉ? ይሄንን ለማለት የሚያስችልዎት እርስዎ ባሉበት አካባቢና በተቀረው የኢትዮጵያ ክፍል መካከል የተፈጠረ ይሄንን ያህል አማረው ሊያወሩት የሚችሉት ነገር ምንድን ነው? ተብለው ቢጠየቁ ምን ብለው ሊመልሱ ነው በፓንዶራ የአጋንንት ሳጥን እስከመመሰል ያደረሰዎት? ትንሽ እንኳን ይታዘቡኛል ምን ይሉኛል አይሉም? እስኪ በሞቴ ይሄ ይሄ ይሄ ብለው ቆጥረው ይንገሩን? አሁን ምንም ማለት አልፈልግም ይሄ ይሄ ብለው የተናገሩ ዕለት ግን በሚገባ የምልዎት ነገር ይኖራል፡፡ ምንም ነገር ሳይናገሩ በደፈናው አጨፍግገው አከፋፍተው በመናገር በዜጎችዎ ጭንቅላት ውስጥ ስለ ኢትዮጵያና ሕዝቧ መጥፎ ሥዕል በመሳል ያንን ዘመን እንዲጠሉ ለማድረግ የሚያደርጉትን ጥረት ግን ቢተውት ይሻላል፡፡ አለዛ ግን ከፆታ ልዩነት በስተቀር ፓንዶራን እራሷን ሆነው እየተወኑ እንደሆን ልብ ሊሉት ይገባል፡፡

በጣም የሚገርመው አቶ ኢሳይያስን የሚያኮራቸው ሲያወሩትም ደስ የሚላቸው ዋጋ የሚሰጡትና የሚወዱት ከ19ኛው መቶ ክ/ዘ በፊት የነበረውን የነጻነቱን የአንድነቱንና ብርቅየውን የፍቅሩን አኩሪውን የሚያስቀናውን ታሪክ ሳይሆን ከ19ኛው መቶ ከ/ዘ ወዲህ ያለው የባርነቱን፣ እንደ ሰው ሳይሆን እንደ እንስሳ ተቆጥረው የተገጠቡበትን፣ ሰብአዊ ክብራቸው ተገፎ እንደ ዕቃ የተቆጠሩበትን፣ የሰቆቃውን የውርደቱን ዘመን መሆኑ ሰውየው ያለበትን የሞራል (የቅስም) ደረጃ ዝቅጠት ውድቀትና ኪሳራ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ እጅግ ይገርማል የሚያሳፍረው ያኮራዋል ሲያወራውም ያስደስተዋል የሚያኮራው ግን ያሳፍረዋል ጨርሶም ሊያወራው አይፈልግም፡፡ አይገርምም? “ለምን ምን አይጥማትም” ነበር ያለው ያገሬ ሰው? ይህ አስተሳሰብ የአጠቃላይ የሕዝቡ እንዳልሆነ ተስፋ ላድርግ ይሆን? እኔ የምልዎ አቶ ኢሳይያስ እርስዎና መሰሎችዎ እንዲያው ከቅኝ ግዛት ምን ብትጠቀሙ ነው ለቅኝ ግዛት ያላቹህ ፍቅር ይሄንን ያህል የቅኝ ግዛትን ውርስ ለማስጠበቅ መሥዋዕትነት እስከመክፈል ድረስ ያደረሳቹህ? ባንዳነት እኮ ያሳፍራል! አያሳፍርም እንዴ አቶ ኢሳይያስ? ለእናንተ እንጃ ለኛ ለነጻነት ታላቅ ቦታና ዋጋ ለምንሰጠው ለሱም ምንም የምስሰስተው ነገር ለሌለን ኢትዮጵያዊያን ግን እጅግ አሳፋሪ አስነዋሪ አዋራጅ ርካሽ ወራዳ ማንነት ነው፡፡

አቶ ኢሳይያስ ቅኝ ገዢዎች ኢትዮጵያን ከሦስት ሊከፍሏት ፈልገው የነበሩት ለምን ይመስልዎታል? የባርነትዎን ውርስ እንደታላቅ ቅርስ እስከ መጨረሻው ለመጠበቅ ቁርጠኛ በመሆንዎ ሕዝብዎ ካላፈረብዎት በሌላ በምንም የሚያፍር አይሆንም፡፡ ከሽዎች ዓመታቱ የአንድነት የከበረ ታሪካችን ይልቅ ለ60 ዓመታቱ የባርነት የጭቆና ታሪክ ይንሰፈሰፉለታል ይንገበገቡለታል ያስቡለታል ይሄ በፍጹም የጤና አይደለም፡፡ ጤነኛ ሰው እንዴት ከወንድሙ ይልቅ በመረረ ግፍና ጭቆና እንደ አሕያ ሲገጥበው የኖረውን ጠላት ይወዳል? ምን እያልኩዎት እንደሆነ ይገባዎታል አቶ ኢሳይያስ? የባርነትን ውርስ በመጠበቅ በመንከባከብ እያስፈጸሙ ያሉት የነዚያን ግፈኞች አረመኔዎች የቅኝ ገዥዎችን ዕቅድና ዓላማ ነው ይሄ ደግሞ ባንዳነት ነው ባርነት ነው ነጻ ወጥቻለሁ ነጻ ነኝ ብለው እንዳያስቡ፡፡ ጭንቅላት ቢኖርዎት ማሰብ ቢችሉ በዚህ እጅግ ሊያፍሩ ሊሸማቀቁ እንጂ እያየንዎት እንዳለው ሊኮሩ ሊኮፈሱ አይገባም ነው እያልኩዎት ያለሁት፡፡ ይሄ ይገባዎት ይሆን አቶ ኢሳይያስ? ሕዝብዎንስ ይገባው ይሆን? እርግጠኛ ባልሆንም ታፍነው ተይዘው እንጅ የሚገባቸው ይኖራሉ ብየ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ግፈኞቹ ቅኝ ገዥዎች ባሕረ ምድርን ከኢትዮጵያ ቆርጠው ይዘው ነበር ዛሬ እነሱ የሉም፡፡ እነሱ በሌሉበት ሁኔታ የግፈኞችን ሕልምና ዓላማ ውርስ በማስቀጠል ባሕረ ምድርን ከኢትዮጵያ እንደተቆረጠች ለማስቀረት መጣር የፋሽስት ዝግንትል ተሸካሚነት (አህያነት) አይደለም ወይ? የሄስ አያሳፍርም ወይ? ያውም እኮ የሚያዋጣ በሆነ ምንም ባልነበር ነገር ግን ጨርሶ የማያዋጣ በሆነበት ሁሌታ እንዲህ መሆን ከአህያም አህያነት አይደለም ወይ? እኔ ምንም አልገባ አለኝ እንዴት ነው የምታስቡት?

እናንተ ብዙ ጊዜ የምታነሡት ነገር አለ “ዐፄ ምንሊክ ሸጠውናል ተከድተናል” የሚል ስለ እውነት ለመናገር ታሪክ ያነበበ በወቅቱ የሆነውን በሚገባ የተረዳ ሰው የሚያስብና የሚያገናዝብ ጭንቅላት ያለው ሰው በእርግጠኝነት ይሄንን አይልም፡፡ የእናንተ ችግር ሲጀመር ታሪኩን የነበረውን ሁኔታ በንጹሕ ሕሊና ለማየት አለመሞከራቹህ አለመፈለጋቹህ ነው፡፡ ይሄንን ለማለት የሚያስደፍረኝ ነገር ከአድዋ ጦርነት ዋዜማ በኢትዮጵያ ምን ተከስቶ እንደነበር ያውቃሉ? “ክፉ ቀን” በመባል የሚታወቀው በሀገሪቱ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የድርቅ ሳይሆን የረሀብ ወቅት ነበር፡፡ ድርቅ ሳይኖር እንዴት ያውም ከባድ ረሀብ ሊኖር ቻለ ይሉ ይሆናል፡፡ የዚህ ምክንያቱ ረሀቡ የተፈጠረው በሰው ሰራሽ ችግር እንጅ በተፈጥሮ አለመሆኑ ነው፡፡ ረሀቡ የተፈጠረው ጣሊያን ከጦርነቱ ከዓመታት በፊት ሀገሪቱንና ሕዝቧን ለቅኝ ግዛት እጅ እንዲሰጡ ለማድረግ የከብት በሽታ ከህንድ አስገብቶ ከብቶችን በመውጋት ከብቱ ሁሉ እንዲያል ስላደረገ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ነው እጅግ አስከፊው “ክፉ ቀን” የሚባለው ረሀብ ሊከሰት የቻለው፡፡ የግብርናው አከርካሪ በመሰበሩ ምክንያት፡፡ “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንዲሉ ሕዝባችን በዚህ መከራ ላይ እያለ ነበር የአድዋ ጦርነት የመጣው ሀበሻ ከነጻነቱ የሚያደርሰውና ለነጻነቱ የማይከፍለው የመሥዋዕትነት ዓይነት ባለመኖሩ በረሀብ የደከመ የኮሰመነ ጉልበቱን ይዞ ነገር ግን እንደ አሳተጎመራ የሚፋጅ የሚገነፍል ወኔውንና የሀገር ፍቅሩን ይዞ ነበር ወደ አድዋ የዘመተው፡፡ ከድሉ በሏላ ገፍቶ በመሔድ ባሕረ ምድርንም ማስለቀቅ ጠፍቶት አልነበረም በመቶ ዐሥር ሽህ ከሚቆጠረው ዘማች (በእርግጥ ጣሊያኖች ቁጥሩን እስከ 160 ሽህ ድረስ ያደርሱታል በቁጥር ብልጫ ስለተወሰደብን ነው የተሸነፍነው ለማለት ነው እንጅ ሐሰት ነው) ከዚህ ሠራዊት ከፊሉ ለአርበኞች ምግብ የሚያበስሉ ሲቆስሉ የሚንከባከቡና የተለያየ አገልግሎት የሚሰጡ ሴቶችና የሚቆዩበት ባለመኖሩ ከወላጆቻቸው ጋር የሔዱ ሕፃናት ናቸው፣ ከሃያ ሽህ በላይ የሚሆነው በጦርነቱ የተሠዋና ቁስለኛ ነበር፣ ሠራዊቱ ስንቅ ጨርሷል ለመሰንበቻ ያህል ከአካባቢው ሰው ለመሸመት ቢፈለግም አንዲት እፍኝ እንኳን ሊገኝ አልቻለም፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይ የነበረ ሠራዊት እንዴት ብሎ ነው ገፍቶ በመሔድ ምናልባትም ከአድዋ የከበደ ጦርነትን ሊያደርግ የሚችለው? ነው ወይስ ተሸንፎ መላዋ ኢትዮጵያ በባርነት ሥር መውደቅ ነበረባት ማለታቹህ ነው?

በዚህ ላይ ደግሞ በጣም የሚገርመውና ሳልነግርዎት ማለፍ የማልፈልገው ነገር ከጣሊያን ወራሪ ሠራዊት ውስጥ ከዓረቦችና ከጣሊያኖች በላቀ ቁጥር በባንዳነት ከጣሊያን ጋር ተሰልፎ የገዛ ሀገሩንና ወገኑን ይወጋ የነበረው የእርስዎ ወገኖች እንደነበሩ ያውቁ ይሆን? ይሄንንም ግንዛቤ ውስጥ ብታስገቡ መልካም ነው፡፡ እናንተ የምታግዙ ቢሆን ነገሩ ምንኛ ቀላል በነበረ ነበር የሆነው ግን ሌላ ነው እናንተም እራሳቹህ ከጣሊያን ጋር ተሰልፋቹህ ሀገር ወገናቹህን የምትወጉበት ሁኔታ ነው የነበረው፡፡ ይሄ ይሄ ሁሉ እያለ አይከብድም አቶ ኢሳይያስ? ስለዚህ ያለው አማራጭ መመለስና ጣሊያንን በውልና በአንዳንድ ነገሮች እዛው ባለበት አስሮ ለማቆየት ጥረት በማድረግ ዕረፍት ወስዶና ጊዜ ወስዶ ተጠናክሮ መመለሱ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ስለሆነባቸው ነው የተመለሱት፡፡

አቶ ኢሳይያስ እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቅዎት አምላክ ታደገን እንጅ ፋሽስት ጣሊያንን የ1928ቱ ወረራው ወደ ቅኝ ግዛት አሸጋግሮት መላዋን ኢትዮጵያን ቅኝ መግዛት ችሎ ቢሆንና ሀገራችን እንደሌሎቹ ሀገራት ከጊዜ በኋላ ነጻ ወጥታ ቢሆን ኖሮ ይሄንን የጠቀሱትን የአፍሪክ አንድነት ድርጅት አዋጅ ያነሡ ወይም ማንሣት ይችሉ ነበር? አዩ አይደል ለዚህ ነው የባርነትን ውርስ ለመጠበቅ ለመንከባከብ ህያው ለማድረግ የሚሠሩ ባሪያ ነዎት የምልዎት፡፡ እያልኩዎት ያለሁት ነገር ይገባዎታል? እያልኩ ያለሁት እርስዎ የሚሉትን ነገር ሁሉ ፋሽስት ጣሊያን ከ40 ዓመታት በኋላ በ1928 ባደረገው ወረራ እንዳይሠራ አድርጎታል ነው እያልኩዎት ያለሁት፡፡ ሰው እንዴት ከባርነት ጋር ፍቅር ይወድቃል? ኧረ እባካቹህ ንቁ በእናንተ ይብቃ ልጆቻቹህንም የባርነት አስተሳሰብ ሰለባ አታድርጓቸው ነጻ ይውጡ ሰዎች እንጅ ጣሊያን ሲገጥባቸው እንደነበሩት አያቶቻቸው ባሪያዎችና የቅኝ ገዥ አጋሰሶች አታድርጓቸው፡፡

በተለይ ደግሞ ሊያስቡ የሚገባው ነገር በሌሎች የአፍሪካ ሀገራትና በቅኝ ገዥዎቻቸው መሀከል የነበረው ሁኔታና ግንኙነት በኢትዮጵያና በጣሊያን መሀከል ከነበረው ሁኔታና ግንኙነት ፍጹም የተለያየና ምንም የሚያገናኘው ነገር ስለሌለ “የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አዋጅ” እያሉ የሚጠቅሱት ድንጋጌ እኛን አይገዛንም በእኛ ላይ አይሠራም፡፡ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ለአንድ ሀገር ብሎ የተለየ አዋጅ ማውጣት ስለሌለበት ሁኔታው በግልጽ ስለሚታወቅ ማንም ሊገነዘበው ስለሚችል ነው የተለየ ሕግ ለኢትዮጵያ ያላወጡት፡፡ በእኛና በጣሊያን መሀከል የነበረው ነባራዊ ሁኔታ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች የተለየ በመሆኑ፡፡ ስለሆነም ይሄንን አዋጅ እንደመተማመኛ ሰነድ አድርገው መቁጠርዎን ያቆማሉ፡፡ እስኪ ሌላ ጥያቄ ልጠይቅዎት ይህ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አዋጅ በሶማሊያ ላይ ለምን ያልሠራ ይመስልዎታል? እንደ እርስዎ እምነት ቢሆን ኖሮ እኮ ሶማሊያ ሁለት ሀገር መሆን ነበረባት፡፡ የእንግሊዝ ሶማሌ (ሶማሌ ላንድ) እና የጣሊያን ሶማሌ ተብለው የተለያዩ ሀገራት መሆን ነበረባቸው፡፡ ነገር ግን ያ አልሆነም፡፡ አሁን ሶማሊያ ከፈራረሰች በኋላ ሶማሌ ላንድ “እኔ ሰላም ነኝ እራሴን ችየ ተነጥያለሁ እራሴንም እያሥተዳደርኩ ነኝ እባካቹህ ዕውቅና ይገባኛል እውቅና ስጡኝ?” እያለች ስትጮህ የአፍሪካ ኅብረትን ጨምሮ ምዕራባዊያን የተቀረውም የዓለም ክፍል ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ዕውቅናውን የነፈጋት ለምን ይመስልዎታል? ስለሆነም ዐሥሬ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አዋጅ እያሉ አያላዝኑብን እንኳንና በኛ በነጻዋ ሀገር በሱማሌም አልሠራም፡፡ ለዚህም ነው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባሕረ ምድርን ወደ እናት ሀገሯ እንድትቀላቀል የወሰነው፡፡

እኛ እኮ እንዲያው የአባቶቻችንን አዳራ ለመጠበቅ የሀገራችንን የግዛት አንድነት ላለማስደፈር ያስረከቡንን እንደተረከብን አድርገን ለተከታይ ትውልድ ለማስረከብ  በሚል ነው እንጅ እኮ እንዲህ የምንንገበገበው አንዳች ጥቅም ኖሯቹህ እኮ አይደለም፡፡ እንኳን ለኛ እራሳቹህ ለራሳቹህ እንኳን እንዳልጠቀማቹህ እያያቹህት ነው፡፡ እናም አደራ ለመጠበቅ ስንል ብቻ በሕገ ወጥ መንገድ ከእናት ሀገሯ የተቆረጠችውን ባሕረ ምድርን ወደ እናት ሀገሯ እንመልሳታለን፡፡ በክህደት የተመረዛቹህና ኢትዮጵያዊያን አይደለንም ኢትዮጵያዊ መሆን አንፈልግም የምትሉ ካላቹህ ተጠራርጋቹህ ቀይ ባሕር ልትገቡ ትችላላቹህ፡፡ መሬታችንን ግን እናት አባቶቻችን ደምና አጥንታቸውን ያፈሰሱ የከሰከሱበትን ምድር ግን እንመልሳለን፡፡ ካዘንንላቹህ ደግሞ አላግባብ በወያኔ የክህደት ሥራ በልግስና የተሰጣቹህን አሰብን ወደ ሀገሩ መልሰን “መንገዱን ጨርቅ ያርግላቹህ” ብለን መርቀን እንሸኛቹሀለን የት እንደምትደርሱ እናያለን፡፡ ከዚያ በኋላ ግን “ኧረ ኢትዮጵያዊያን ነን መልሱን እሪ ያገር ያለህ” ብትሉም እንኳ አንፈልግም ይህ የናንተ ትውልድ ለመገንጠል ብረት እንዳነሣ ሁሉ ቀጣዩ ትውልዳቹህ ደግሞ ለመዋሐድ ብረት የሚያነሣ ይሆናል፡፡

እንግዲህ አቶ ኢሳይያስ በቃለመጠይቃቸው የቀበጣጠሩት የባጥ የቆጡንና የተንዛዛም ስለነበር ተንዛዝተው ሲያበቁ እኔንም አንዛዙኝ፡፡ በሌላው ጉዳይም ሁሉ መልስ ልስጥ ብል እሳቸውን መሆን ስለሚሆን በዚሁ ይብቃኝ፡፡ ከመቋጨቴ በፊት ግን በትጥቅ ትግል እዚያ ላሉ ወገኖቻችን የማስተላልፈው መልዕክት አለኝ፡- ወገኖቸ ሸአቢያ ሸአቢያ ነው፡፡ መቸም ቢሆን ከሸአቢያነቱ ሊለወጥ አይችልም፡፡ ሸአቢያን ከሸአቢያነቱ ወያኔንንም ከወያኔነቱ መለወጥ ማለት ሰይጣንን ወደ መልአክነት መለወጥ መቻል ማለት ነው ፈጽሞ የማይቻል የማይሆን ነገር ነው፡፡ ስለሆነም በምንም ተአምር ቢሆን በሸአቢያ ላይ እምነት እንዳትጥሉ፡፡ አማራጭ የለምና የትጥቅ ትግሉን እዚያው ማድረግ ግድ ነው፡፡ ሸአቢያ ይሄንን ዕድል በመስጠቱ ውለታ እንደሠራልን እንዳትቆጥሩት፡፡ እሱ ሊያደርገው የማይችለውንና መቸም የማያገኘውን ዕድል ነው በእናንተ ምክንያት ያገኘው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ልብና ድጋፍ ከእናንተ ጋር ነው ይሄ ማለት በወያኔና በሸአቢያ መሀከል ጦርነት ቢነሣ እንደ ባለፈው ሁሉ ሕዝቡ ሆ ብሎ ከወያኔ ጋራ ተሰልፎ ሸአቢያን አይወጋም እንኳንና ሕዝቡ ወታደሩም እንኳን ቢሆን ይሄንን አያደርግም ይሄንን የሚያደርገው ለሸአቢያ በማዘን ሳይሆን ለእሱ ስትሉ በረሀ ስለገባቹህት ስለእናንተ ሲል ነው፡፡ ሸአቢያ ለእናንተ ቦታ በመስጠቱ ወይም በመርዳቱ ምክንያት ይሄንን ታላቅ ጥቅምና አጋጣሚ ማግኘት ችሏል በዚህም ምክንያት ከወያኔ ጋራ ጦርነት ቢገጥም በቀላሉ ሊያሸንፍ የሚችልበትን ዕድል አግኝቷል፡፡ ይሄ ነው የውለታው ክፍያ፡፡ ያደረገው ለራሱ ጥቅም ሲል እንጅ ለኛ ወይም ለኢትዮጵያ አይደለም፡፡ መችም መቸም ሊያገኘው የማይችለውን ጠላቱን እንዲበቀል የማድረግ ዕድሉን እንዲያገኝ አድርገናልና ውለታው በዚህ ተመልሷል፡፡ ሌላ ክፍያ ሊጠብቅ አይደለም ሊያስብ እንኳን አይገባም፡፡ ነገር ግን ሸአቢያ ልብና ማስተዋል ጭንቅላት የለውምና እንዲህ ስላደረኩላቹህ ወይም ስለማደርግላቹህ እንዲህ ታደርጉልኛላቹህ እያለ አስጨንቆ ቢይዛቹህ አሽ በሉት ፈርሙም ካላቹህ በዐሥር ጣቶቻቹህ ፈርሙለት ይሄንን ባለማድረጋቹህ እናንተን ማጣት አንፈልግምና፡፡ ልባቹህን እናውቀዋለንና ተገዳቹህ የውሸት የፈረማቹህለትን ፊርማ በመፈረማቹህ ክህደት እንደፈጸማቹህ አንቆጥርም፡፡ ታደርጉልኛላቹህ ያላቹህ ነገር ሊከፈለው የሚችለው እዚህ ሀገራቹህ ገብታቹህ በምድራቹህ ሆናቹህ ወያኔን አስወግዳቹህ ነውና ሊሆን የሚችለው ከሕገ ወጥና ከከሀዲ ጋር የተደረገ ውል አይጸናምና ያኔ አፍንጫህን ላስ ብንለው በሀገራቹህ በምድራቹህ ከወገናቹህ ጋር ሆናቹህ ነውና ምንም ሊያመጣ አይችልም፡፡ በጅብ ሀገር እንደ ጅብ መጮህ ግድ ይላል፡፡ መድኃኔዓለም ከናንተ ጋር ይሁን!!!

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

 

The post አስቂኙ የአቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ቃለ መጠይቅ! – ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

መኢአድ በወያኔ ሚዲያዎች በኢቢሲ በፋና በዛሚ እንዳያቀርበዉ የተከለከለዉ ጽሑፍ

$
0
0

የተወደድክና የተከበርከው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!

aeupከዘመናት በፊት የሥልጣኔ ችቦ ከተቀጣጠለባቸው ጥቂት አገሮች መካከል አገራችን ኢትዮጵያ አንዷ ናት፡፡ በዚህ ረጅም የሥልጣኔና
የታሪክ ዘመን ውስጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ በተለያዩ መንገዶችና በማንኛውም ሁኔታ ነፃነቱን ለማስከበር ከውጭ ወራሪ ሐይሎች
ጋር ሲታገል መኖሩ የዓለምን ሕዝብ ቀልብ ከመሳቡ ባሻገር ለአፍሪካውያንና በዓለም ላይ ላሉ ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት አርአያና
ተመሳሌት በመሆን የጥቁርን ዘር ክንድ ብርታትና ፅኑነቱን አስመስክሯል፡፡ ይህ አስደናቂና ወደር የማይገኝለት ድል ዘወትር
የሚከነክናቸው ባእዳን የሀገር ውስጥ ባንዳዎችን በማዘጋጀትና ግንባር ቀደም ተዋናይ በመሆን ብዙና ከባድ የችግር ቀንበር
ሊጭኑበት ሞክረዋል በዚህ ምክንያት ህዝባችን ዘርፈ ብዙ መስዋዕትነትን እንዳከፍልም ሆኗል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነቱን፣ ታሪኩን፣ ሉዓላዊነቱንና ባህሉን ለሦስት ሺህ ዓመታት ጠብቆ የኖረ መሆኑን ዓለም ይመሰክራል፡፡
ሕዝባችን በውስጥ አስተዳድር የደላውና የተመቸው ባይሆንም ቅሉ ብሶቱን አቻችሎ የአገሩን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት ለማስከበር
ዘር፣ ጐሳ፣ ቀለምና መንደር ሳይለየው በደሙ እየዋጀ መተኪያ የሌላት ሕይወቱንም ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
የኢህአዴግ መንግሥት ሥልጣን ከያዘበት ቀን ጀምሮ ይህን በደምና በአጥንት የተገነባ ዳር ድንበር እንዲጣስ በማድረግ
ለባእድ ፈቅዶ በመሥጠት ወደብ አልባ አድርጐናል፡፡ ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ጥቅም እንዲሁም የሕዝቧን ግለሰባዊና ቡድናዊ
ነጻነትና ደህንነት በተገቢው መንገድ ማስጠበቅ ስላልቻለ ድርጊቱን በመቃወም ለመታገል የመላው ኢትዮጵያ አንድነት
ድርጅት /መኢአድ/ በሕብረ ብሔራዊና አገር አቀፍ ፓርቲነት በቁርጥ ቀን ልጆች ተመሰረተ፡፡
ኢህአዴግ የደርግን መንግሥት ተክቶ ሥልጣን ከያዘበት ቀን ጀምሮ ይመጣል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረውን የአገር አንድነት፣
ሰብአዊ መብት መከበር፣ የዲሞክራሲ መጎልበት ሒደት ቀልብሶ የኢትዮጵያን ሕዝብ ዘርና ቋንቋን መስፈርት ባደረገ የክፍፍል
ቀለበት ውስጥ አስገብቶ እርስ በእርሱ እንዲናቆር የሚአደረግ ሥልት ዘረጋ፡፡ ሕዝባችንም በተወለደባት አገር ከቦታ ቦታ
በመዘዋወር በነጻነት መሥራት እንዳይችል በተደረገበት ወቅት መኢአድ ይህን ለአገርና ለትውልድ የማይበጅ ድርጊት በመቃወም
የኢትዮጵያን ሕዝብ አስተባብሮ ሉአላዊነቷ የተጠበቀ፣ እድገቷ የተፋጠነና የህግ የበላይነት የሰፈነባት ዲሞከራሲያዊት ኢትዮጵያን
ለመገንባት የተቋቋመ አንጋፋ ድርጅት ነው፡፡ መኢአድ የህን ለአገርና ለትውልድ የማይበጅ ሥርዓት ሲታገል
ቆይቷል፤ በመታገል ላይም ይገኛል፡፡ መኢአድ ይህን እንቅስቃሴ ሲያደርግ በነበረበት ወቅትም ትግሉ አልጋ በአልጋ አልነበረምና
የገዥው ፓርቲ ካድሬዎችና አመራሮች በፓርቲው መሪዎች፣ አባላቶችና ደጋፊዎች ላይ ከፍተኛ የሆነና ግፍ የተሞላበት
ድብደባ፣ መሳደድና፣ የመታሰርና የመገደል ዕጣ ሲደርሱባቸው ቆይተዋል፡፡
እጅግ ዘርፈ ብዙ ችግሮች የሚቀየር ቢሆንም የሕዝብ ጥያቄ የሆነውን የነፃነት፣ የሕግ የበላይነት መስፈን፣ የሰብዓዊና
ዲሞክራሲያዊ መብቶች መከበር ለሚደረገው ትግል የኢትዮጵያን ሕዝብ ለመምራት በግንባር ቀደምትነት ብቸኛውና ጥንካሬውን
ያስመሰከረው የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ተስፋ የሆነው መኢአድ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ያደረገው ሕዝባዊ
ትግል የኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን የዓለምን ሕብረተሰብ ትኩረት በመሳብ ላይ ይገኛል፡፡ መኢአድ ከስሙ መረዳት
እንደሚቻለው ሕዝባችን በአንድነት በእኩልነትና በመፈቃቀር እንደኖር አስተማማኝ ፖሊሲዎችን ነድፎ ተግባራዊ ለማድረግ
በመላ አገሪቱ በመንቀሳቀስ ላይ ያለ ሀቀኛ የፖለቲካ ድርጅት ነው፡፡
መኢአድ ይህንን ታሪካዊና ህዝባዊ ሃላፊነት ለመወጣት ሲል በሚያደርገው ሁሉንተናዊ የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ የገዥው
ፓርቲ ኢህአዴግ ከቅድመ ምርጫ 97 ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ በፓርቲው አባላት ላይ ከፍተኛ እንቅፋት መፍጠሩ የቀን ከቀን
ትዕይንት ሆኖ ቀጥሎአል፡፡ ኢህአዴግ ይህን ሁሉ ቢፈጽምም ሚስማር ሲመታ ይጠብቃል እንደሚባለው ሁሉ መኢአድ በአባላቱ
ላይ የሚደርስበትን ዘርፈ ብዙ ተፅዕኖ፣ ችግርና ሰቆቃ በመቋቋም ለሕዝብና ለሀገር የሚጠቅም ሥራ በመስራት የኢትዮጰያን ትንሳኤ
ለማየት ህዝባዊና ሀገራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ላይ ይገኛል፡፡ አሁን በሀገራችን ኢትዮጵያ የሚታዩት ከዚህ ቀደም ያለፉት የገዥ
መደቦች የሕዝብ ምርጫና ሰላማዊ መንገድ የሥልጣን ሽግግር ባለመከናወናቸው ኢህአደግም ያንን በመከተል ከማንወጣው
ችግር ውስጥ እንድንገባ ተደርገናል ያለፉት የገዢው መደቦች ሰላማዊ ነፃና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዳይኖር ሕዝቡን በአንድ
ወጥ የአገዛዝ ቀንበር ከሥረው ያቆዩትን ጨቋኝ ልማድ ኢህአዴግ በመረከብ ከህዝባዊ ምርጫ ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር
እንዳይኖር በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
የኢትዮጵያ ሕዝብ ከብዙ ሺህ አመታት የነፃነት ታሪካችን ባለተናነሰ ሁኔታ በዘር በቋንቋና በጉሳ ሳይለያይ በፍፁም ወንድማማችነት፣
መከባበር፣ መፈቃቀርና መቻቻል አብሮ መኖሩን ታሪክ ይመሰክራል፡፡ ዛሬ የሕዝባችን ችግር ኢህአዴግ እንደሚያራግበው
የክልል፣ የቋንቅ፣ የሀይማኖትና የዘር ልዩነት አይደለም፣ ችግሩ ዳር ድንበራችንን አስጠብቆና አንድነታችንን አጠናክሮ የተለመደ አብሮ
የመኖር የፍቅርና የአንድነት ባህሉን አስጠብቆ ከድህነት ማጥ ውስጥ በማውጣት ለተሻለ ሕይወት ሊያበቃን የሚችል ሐዝብ
የመረጠውና የሕዝብን አመኔታ ያገኘ መንግሥት አለማግኘት ነው፡፡ የኢህአዴግ መንግሥት የኢትዮጵያ ሕዝብ ከአያት ቅድመ አያቱ
ጀምሮ የያዘውንና እትብቱ የተቀበረቡትን መሬት በሀይል ነጥቆ ሕዝባችንን እንደፈለገ የሚነቅለውና የሚተክለው አዲስ አይነት
የመንግሠት ጭሰኛ አድርጎታል፡፡ በገጠርም ሆነ በከተማ የሚገኘው መሬት የኢትዮጵያ ሕዝብ ደሙን ያፈሰሰበት ህይወት
የገበረበት አንጡራ ሀብት ሆኖ እያለ የገዥው ፓርቲ መሬት የመንግሥት እንጂ የሕዝብ የግል ሀብት መሆን አይችልም በሚል
ፈሊጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከአባቶቹ የወረሰውን መሬት በኪራይ እንጂ /በጭሰኝነት/ በባለቤትነት በመያዝ ለልጁ እንዳያወርስ፣
እንዳይሸጥና እንዳይለውጥ በአዋጅ ከልክሏል፡፡ በዚህም የተነሳ የኢህአዴግ መንግሥት የመሬትን ፖሊሲ የፖለቲካ ትርፍ
ለማግኘት እየተጠቀመበት ይገኛል፡፡ መሬት ከሀብትም ሁሉ በላይ የሆነ የገበሬው የደምና የአጥንት መስዋዕትነት የተከፈለበት ምትክ
የሌለው ህይወቱ ነው፡፡ ገበሬውም ሆነ ከተሜው ከመኢአድ ጋር ከተጓዝክ የገጠር መሬት በግል ባለበትነት እንዲያዝ ትታገላለህ
ለድልም ትበቃለህ፣ የከተማ ቦታን ከሊዝ ነፃ በማድረግ የምታዝበት አንጡራ ሀብትህ ታደርጋለህ፣
ሕዝብ በከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ወድቆ እያለ በነጻነት እንደፈለገው በመንቀሳቀስ ለአገሩ እድገትና ለሕዝቡም ብልጽግና ይሰራል
ማለት አይቻልም መንግሥትም ያምናል ማለት የሕዝብን እውቀት፣ ጉልበትና ሀብት አስተባብሮ ለአገር ልማት ለማዋል በመጀመሪያ
ደረጃ አንዱን ልጅ ሌላውን የእንጀራ ልጅ አድርጎ የሚገዛ መንግሥት ሳይሆን የአገሪቱን ሕዝብ ያሳተፈ፣ ፍትሀዊ የሆነና
ከሙስናና ከአድልኦ የጸዳ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ፖሊሲ በአስተማማኝ ሁኔታ መመሥረት ሲቻል ነው፡፡
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ይህን ክፍተት በመሙላት የኢትዮጵያን ሕዝብ በአንድነት፣ በእኩልነትና ፍትህ
በተሞላበት ሁኔታ በመምራት ለነጻነት ለማብቃት በመታገል ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም መኢአድ በ1997 በቅንጅት ከሌሎች
ኃይሎች ጋር በተሰለፈበት ወቅት በደረሰበት በደልና ግፍ ተስፋ ሳይቆርጥ ባለው ከፍተኛ ህዝባዊ ተቀባይነት የተነሳ በአሁኑ ሰዓት
በመላው ሀገሪቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቢሮዎችን በመክፈት ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በዕኩልነት በማሳተፍ ላይ ነው፡፡ በዚህ
የአንድነትና የነጻነት ትግል እንቅስቃሴ የሁሉንም ኢትዮጵያውያን መብት ለማስከበር ከሁሉም ጋር ጥብቅ የሆነ ግንኙነት ፈጥሮ
ተስፋ የተጣለበት ሥራ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ በመላ ሀገሪቱ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ፣
ከርዕሰ ከተማ እስከ ቀበሌ ድረስ በመውረድ ህብረተሰቡን በማደራጀትና በማንቃት፣ ህዝቡ ስለሀገሩ አንድነት፣ ነፃነትና
የዲሞክራሲ ፅንሰ ሀሳብ ግንዛቤ እንዲያዳብር በማድግ ከፍተኛ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል፡፡ የፓርቲው እንቅስቃሴ በሀገር
ውስጥ ብቻ የተወሰነ ባለመሆኑ በተለያዩ ምክንያቶችና መንገድ ሀገራቸውን ጥለው በባዕድ ሀገር በስደት የሚኖሩትን
ኢትዮጵያውያን ጭምር ስለሀገራቸውና ህዝባቸው ማድረግ ያለባቸውን ሁሉ ሀላፊነት በመፈጸም የነፃነት ትግሉ ተሳታፊዎች
ከመሆን አልፈው ባለቤት ጭምር እንዲሆኑ አድርጓል፤ በማድግ ላይም ይገኛል፡፡
መኢአድ በዓለም ላይ ባሉ በርካታ ሀገሮች ተሞክሮ ውጤታማነቱ በተረጋገጠው የሌቨራል ዲሞክራሲ ጽንሰ ሀሳብ ላይ የተመሰረተ
የፖለቲካ ፍልስፍና የሚከተል ፓርቲ ነው፡፡ በዚሁ መሠረት መኢአድ ዋና ግቡ በአገራችን ስልጣን በህዝብ እጅ እንዲገባና ባጭር ጊዜ
ውስጥ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት በመገንባት፣ ፍትህና የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ፣ ለህዝባችን ደህንነትና ልማት ዋስትና
ሊሰጥ የሚችል፤ ባጠቃላይ ለህዝብ መብት መከበር የቆመ መንግሥት መመስረት ነው፡፡ የመኢአድ ተልኮ የኢትዮጵያን ሕዝብ
በነፃዊ ዲሞክራሲ መርህ መሰረት በመምራት የስልጣን አመንጭነቱን፤ ባለቤትነቱንና ተቆጣጣሪነቱን በማረጋገጥ
የበለፀገች ጠንካራ ኢትዮጵያን መገንባት ነው፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
አሁንም ሆነ ወደፊት በቆራጥነት፣ በሙሉ ልብና ብሩህ ተስፋ በተሞላበት ሁኔታ እጅ ለእጅ ተያይዘን በሀገራችን ላይ በአንድነት
የነፃነት ችቦ እንደናበራ ከፓርቲህ ከመኢአድ ጐን እንድትሰለፍ ሀገራዊ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
1. የመጀመሪያው ምርጫ የአሸናፊነቱን መንግሥት መመሥረት ነው፡፡
2. ለዜጋና ለሀገር ከፍተኛ አገልግሎት የሚሰጡ ምሁራንን ከሌሎች ፓርቲዎችም ሆነ ግለሰቦች በመንግሥት መዋቅር ውስጥ
ተሳታፊ እንዲሆኑ ይጥራል ነው፡፡
የመኢአድ የፖለቲካ ፍልስፍናና የወደፊት ራዕይ እንደሚከተለው ይሆናል፡፡
1. ፓርቲያችን በምርጫ የበላይነት ሲቀናጅ ሐገራችንን በጋራና በሕብረት ለመገንባት እንዲቻል እንዳስፈላጊነቱ ከአንድ ወይም
ከዚህ በላይ ከሆኑ ዲሞራሲያዊ ከሆኑት ፓርቲዎች ጋር የጥምር መንግሥት ያቋቁማል፡፡
2. ወቅቱን ጠብቆ በሚከናወነው ምርጫ አንድ ሰው አንድ ድምጽ በሚል የሊበራል ዲሞክራሲ መርሀ መሠረት በግለጽ፣ በነጻና
በፍትሐዊ ምርጫ የሕዝቡን የሥልጣን አመንጭነት በባለቤትነትና በተቆጣጣሪነት ለማረጋገጥ መኢአድ የበኩሉን ሁሉ ያደርጎል፡፡
3. ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጐች የተለያዩ እምነቶችና የፖለቲካ አመለካከቶች በነጻነት ማራመድና ልዩነቶቻቸውን አቻችለው መኖር
የሚችሉበት አመቺ ሁኔታን ለመፍጠር መኢአድ የበኩሉን ጥረት ያማርጋል፡፡
4. ሕግ አስፈጻሚ አካል በቀጥታ በሕዝብ በሚመረጥና የሥልጣን ዘመኑ በሕግ በተገደበ ኘሬዝዳንት የሚዋቀርና የመከላከያ ኃይል
ተጠሪነቱ ለኘሬዝዳንቱ እንዲሆን ይደረጋል፡፡ ይሁን እንጂ የመከላከያ ኃይሉ ለፖለቲካ ጉደይ መጠቀሚያ እንዲውል
አይደረግም፡፡
5. የብሔረሰቦች ክልል ያለ ሕዝብ ጥያቄና ያለ ሕዝቡ ውሳኔ /referendum/ የማይቀየር የማይለወጥ ቢሆንም ማንም
ኢትዮጵያዊ በፈለገበት አካባቢ የመኖር፣ የመስራት፣ ሐብት የማፍራት ወዘተ… መብቱ የተጠበቀና የተከበረ እንዲሆን
ይደረጋል፡፡
6. ማንኛውም ሰው በሕይወት የመኖር መብቱ፣ የአካል ደሕንነቱና ነጻነቱ ፍፁም የማይጣስና የማይገሰስ መሆኑን መኢአድ ያምናል፤
ለተግባራዊነቱም ይታገላል፡፡
7. ማንኛዋም ሰው ከሕግ አግባብ ውጭ አይያዝም፣ አይታሰርም፣ አይቀጣም እንዲሁም ሰውነቱም ሆነ የግል ንብረቱ ከሕግ አግባብ
ውጭ አይፈተሽም፣ አይወሰድም፡፡
8. መኢአድ የሌሎች ድርጅቶችን ሕጋዊ ሕልውና የሚያከብር ሲሆን በተለያዩ አስገዳጅ ምክንያቶች በትጥቅ ትግልና በስደት ላይ
የሚገኙ የፖለቲካ ቡድኖችና ሌሎች ወገኖቻችንን ሰላማዊና በሕዝባዊ ፖለቲካ መንገድ መሳተፍ እንዲሳተፉ ሐገራዊ የድርድር
መድረክ እንዲመቻች ሁሉን አቀፍ የሆነ የፖለቲካ ሥርአት እንዲሰፍን የማያቋርጥ ጥረት ያደርጋል፡፡
9. ሊብራል ዲሞክራሲ በሰፈነባቸው የበለፀጉ ሐገሮች መገናኛ ብዙሃን እንደ አራተኛ የመንግሥት ዘርፍ ይቆጠራል፡፡ በኢትዮጵያም
ተመሳሳይ ሁኔታ እንዲፈጠር መኢአድ ከፍተኛ ጥረት ያደርጋል፡፡

The post መኢአድ በወያኔ ሚዲያዎች በኢቢሲ በፋና በዛሚ እንዳያቀርበዉ የተከለከለዉ ጽሑፍ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

የተሽከርካሪ አደጋ መብዛት ያሳሰበው መንግሥት ለባለድርሻዎች ጥሪ አቀረበ

$
0
0

-ባለፉት ስድስት ወራት በአዲስ አበባ ብቻ 260 ሰዎች ሞተዋል

-ከ81 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል

katelo 3ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ የመጣው በተሽከርካሪ አደጋዎች በሰውና በንብረት ላይ የሚያደርሱት ጉዳት እያሳሰበው የመጣው መንግሥት፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር አደጋን በተመለከተ ትኩረት ሰጥቶ ለመሥራት ጥሪ አቀረበ፡፡

የተሽከርካሪ አደጋ ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ከመቅጠፉም በተጨማሪ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖው ከፍተኛ መሆኑን በመጠቆም መንግሥት፣ ኅብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት ተባብረው መሥራት የግድ እንደሚላቸው የፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ደመላሽ ገብረ ሚካኤል አሳስበዋል፡፡

የተሽከርካሪ አደጋ በአዲስ አበባ ወይም በከተሞች ብቻ ሳይሆን፣ በፌዴራል ደረጃ አሳሳቢ እየሆነና በየጊዜው መጠኑ እየጨመረ መሆኑን የጠቆሙት ምክትል ኮሚሽነሩ፣ ሁሉም ተባብሮና ትኩረት ሰጥቶ በመሥራት ችግሩን መቀነስ ካልቻለ አሳሳቢ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ባለንብረቱ፣ አሽከርካሪው፣ ኅብረተሰቡና ትራፊክ ፖሊስ ተባብረው የችግሩን መንስዔ በደንብ በማጥናትና መፍትሔ በመፈለግ፣ ችግሩን መቀነስና ማቆም እንደሚገባ ጠቁመው፣ መንግሥትም በጉዳዩ አሳሳቢነት ላይ ትኩረት ሰጥቶ ለመሥራት ቁርጠኛ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ባለፉት ስድስት ወራት የ260 ሰዎች ሕይወት በተሽከርካሪ አደጋ ማለፉን የጠቆሙት ደግሞ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ ፖሊስ ሕዝብ ግንኙነት ረዳት ባለሙያ፣ ረዳት ኢንስፔክተር አሰፋ መዝገቡ ናቸው፡፡ በስድስት ወራት ውስጥ የ196 ወንዶችና የ64 ሴቶች ሕይወት እንዲያልፍ ያደረገው የተሽከርካሪ አደጋ፣ ከ81 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረትም እንዲወድም ማድረጉንም አስረድተዋል፡፡

አሽከርካሪዎች ራሳቸውን ለመከላከል የሚፈልጉት ትራፊክ ፖሊስ ከሚጥልባቸው ቅጣት እንጂ፣ ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ለመጠበቅ አለመሆኑን የገለጹት ረዳት ኢንስፔክተር አሰፋ፣ ከጥቂት ጨዋና ሕጉ የገባቸው ሕግ አክባሪ አሽከርካሪዎች በስተቀር፣ አብዛኛዎቹ ሕግ ለማክበር ወይም ለሕዝብ አሳቢ የሚመስሉት ትራፊክ ፖሊስ ቆሞ ሲያዩ ብቻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

እየደረሰ ያለውን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ ከትራፊክ ፖሊስ በተጨማሪ ዓለም የደረሰባቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም ቁጥጥሩን ማዘመን አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን የተናገሩት ባለሙያው፣ ሲሲቲቪ ካሜራና ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም፣ የትራፊክ ፖሊስ በሌለበት ቦታ ሁሉ ቁጥጥር ማድረግ አማራጭ የሌለው መፍትሔ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በተለይ በቅርብ ጊዜ ወደ አገር ውስጥ የገባው የቻይና ሥሪት የሆነው ሲኖትራክ የጭነት ተሽከርካሪ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ፣ ፌዴራል ትራንስፖርት ባለሥልጣን ልዩ የቴክኒክ ቡድን በማቋቋም የችግሩን መንስዔ ለማጥናት በዝግጅት ላይ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ግን ባለሥልጣኑ የያዘውን አቅጣጫ በመቃወም አስተያየታቸውን ለሪፖርተር ሰጥተዋል፡፡

ተሽከርካሪው (ሲኖትራክ) በራሱ ምንም ዓይነት ችግር እንደሌለበት የሚናገሩት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ በኢትዮጵያ በተለይ አሁን እየተሠሩ ባሉ የመንገድ ግንባታዎች ላይ የተሰማሩ በርካታ ሲኖትራክ ተሽከርካሪዎች፣ በአንዳንድ ብቃት ባላቸው ኢትዮጵያውያን አሽከርካሪዎችና ቻይናውያን በአግባቡ እየተገለገሉበት ነው ብለው፣ ተሽከርካሪው ካለው ጉልበት የተነሳ ለሥራው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ተሽከርካሪው በቴክኒክም ሆነ በይዘት በኩል ችግር እንደሌለበት ተናግረዋል፡፡ ነገር ግን በተቃራኒው በየዕለቱ በተለይ በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ የተሽከርካሪ አደጋ እየደረሰ ያለው በሲኖትራክ መሆኑን የሚናገሩት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ ‹‹ይኼ የሚያሳየው የተሽከርካሪውን ሳይሆን የአሽከርካሪዎችን ችግር መሆኑን ነው፤›› ሲሉ ችግሩ የአሽከርካሪዎች መሆኑን ያስረዳሉ፡፡

አንድ አሽከርካሪ ሁለተኛ የመንጃ ፈቃድ (ቀላል አውቶሞቢሎችን ለማሽከርከር የሚያስችል) ለማውጣት የትራፊክ ደንቦችንና ምልክቶችን ከማጥናቱም በተጨማሪ፣ የማሽከርከር ብቃቱን በደንብ የሚለካበት ሥልጠና ወስዶ፣ ሁለቴና ከዚያም በላይ በተግባር ፈተና ወድቆ፣ በደንብ ከሠለጠነ በኋላ ያገኝ እንደነበር አስተያየት ሰጪዎቹ አስታውሰዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ግን አንድ አሽከርካሪ ራሱ ካልፈራ በስተቀር በአንድ ጊዜ አምስተኛ መንጃ ፈቃድ የሚያገኝበት ዕድል እንደተፈጠረለት ጠቁመው፣ ‹‹እንኳን ሲኖትራክን ቀርቶ ቀላል የቤት አውቶሞቢልን የማሽከርከር ብቃት አይኖረውም፤›› ሲሉ፣ የችግሩ መንስዔ የአሽከርካሪዎች ብቃት ማነስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የተሽከርካሪውን የቴክኒክ ብቃት ለማስጠናት ኮሚቴ በማቋቋምና የቴክኖሎጂ ውጤት የሆነውን ተሽከርካሪ ለማጥናት ከማሰብ ይልቅ የአሽከርካሪዎቹን የማሽከርከር ብቃት፣ የመንጃ ፈቃድ ትምህርት ቤቶች የማሠልጠን ብቃት፣ የትራፊክ ፖሊሶች የመቆጣጠር ብቃትና የመንገዶችን ብቃት ማጥናቱ የተሻለ እንደሚሆን መክረዋል፡፡

ረዳት ኢንስፔክተር አሰፋ መዝገቡና ረዳት ኮሚሽነር ደመላሽ ገብረ ሚካኤልም አስተያየት ከሰጡት የኅብረተሰብ አካሎች ጋር ተመሳሳይነት ያለው አስተያየት በተለይ በአሽከርካሪዎች ብቃትና በትራፊክ ፖሊሶች ቁጥጥር ላይ አስተያየታቸውን ሰንዝረዋል፡፡ በአፍሪካ የተሽከርካሪዎች ብዛት ከዓለም ሁለት በመቶ የሚሆነውን የሚሸፍን ቢሆንም፣ በአኅጉሪቱ የሚከሰተው አደጋ ግን የ20 በመቶ ድርሻ እንዳለው ጥናቶች እንደሚያመለክቱ አስተያየት ሰጪዎቹ ጠቁመዋል፡፡ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ አገሮች ችግሩ የባሰ ስለሚሆን መንግሥት፣ ኅብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት ተባብረው በመሥራት ችግሩን ማጥፋት ባይችሉ እንኳን መቀነስ ተገቢ መሆኑን አክለዋል፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

The post የተሽከርካሪ አደጋ መብዛት ያሳሰበው መንግሥት ለባለድርሻዎች ጥሪ አቀረበ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ሶስት ሚሊየን ብር የሚጠጋ ወጭ የወጣበት ድልድይ የጥራት ችግር አለበት ተባለ

$
0
0

የካቲት ፳፮(ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአባይ ወንዝ ላይ የተሰራዉ 108 ሜትር ርዝመት እና አንድ ነጥብ ስድስት ሜትር ስፋት ያለው ተንጠልጣይ ድልድይ በሃገሪቱ ብቸኛዉ የተንጠልጣይ ድልድይ በመስራት በሚታወቀው ሄልቬታስ ሲዊዝ ኢንተርኮኦፕሬሽን በተሰኘ መንግስታዊ ባልሆነ ድርጅት ባለፈው ታህሳስ ወር መጨረሻ በይፋ ተመርቆ ስራ ቢጀምርም፣ በምረቃው ስነስርዓት የተገኙ ባለሙያዎች ድልድዩ የጥራት ችግር እንዳለበት መናገራቸው ነዋሪዎችንና በቦታው ተገኙ አመራሮችን አስደንግጧል፡፡

በአማራ ክልል ገጠር መንገድ ስራዎች ድርጅት የቁጥጥርና ክትትል ኬዝ ቲም ባለሙያ የሆኑት አቶ ይገርማል ታምር በዝርዝር ያቀረቡት የጥራት ችግር በምረቃ ስነስርዓቱ ለታደሙ የክልል እና የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ የበጎ አድራጎት ድርጅቱ ኃለፊዎች፣ ግንባታውን በኃላፊነት የሰራው ባለሙያ እና የአካባቢውን ነዋሪዎችን ያስደነገጠ እንደነበር በምረቃው ስነስርዓት የተገኙ ታዛቢዎች ተናግረዋል፡፡

40 በመቶ በሄልቬታስ ፤60 በመቶዉ ደግሞ ከዓለም ባንክ የግብርና እድገት ፕሮግራም በተገኘ ገንዘብ ወጭዉ የተሸፈነው ይህ ድልድይ ለሃምሳ አመታት እንዲያገለግል ታስቦ የተሰራ ቢሆንም የተሰራበት የድንጋይ አይነት፣የውሃ አጠጣጡ እና ገመዶችን ወጥሮ የያዘው የግንባታ አካል ስጋት ያለበት መሆኑን ባለሙያው ተናግረዋል፡፡

የዳስራ ማርያም እና የጭስ አባይ እንዲሁም በደቡብ ጎንደር ዞን ደግሞ የደራ ወረዳ የተወሰኑ የገጠር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደሮችን የዘመናት ጥያቄን የፈታ ሁኗል የተባለለት ታንኳ በር ተንጠልጣይ ድልድይ እንዲሰራ ላለፉት ሁለት ዓመታት አርሶ አደሮች በተደጋጋሚ ለሚመለከተዉ አካል ጥያቄ ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡

ሄልቬታስ ስዊዝ ኢንተርኮርፕሬሽን የተባለው የግብረ ሰናይ ድርጅት በክልሉ በተለያዩ ቦታዎች የሚሰራቸውን ተንጠልጣይ ድልድዮች ስራ በብቸኝነትና ማንም ተቆጣጣሪ በሌለበት ሁኔታ እንደሚሰራና ማኔጅመንቱም በአንድ አካባቢ ሰዎች ብቻ የተያዘ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። ድርጅቱ በአምስት ክልሎች ከስልሳ በላይ ተንጠልጣይ ድልድዮችን እንደሰራ በእለቱ የምረቃ ስነስረአት ላይ ተገልጿል፡፡

Source:: Ethsat

The post ሶስት ሚሊየን ብር የሚጠጋ ወጭ የወጣበት ድልድይ የጥራት ችግር አለበት ተባለ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ማስተርስ/ዶክተሬት እንደ መለዋወጫ እቃ! (ታሪኩ አባዳማ)

$
0
0

ታሪኩ አባዳማ | የካቲት 2007

ልጄ አስራ ሁለተኛ ክፍል ስለጨረሰ የደስታዬ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ… የሚል ግብዣ ደርሷችሁ አያውቅም? እናንተም ፋሽኮ ቪኖ ወይንም እናትና ልጅ አረቄ ይዛችሁ ድግሱን ለማድመቅ ሳትሄዱ አልቀራችሁም – የዚያን ዕለት ጎረምሶቹ የቀለጠ ፓርቲ ደግሰው እስኪነጋ ይጨፍራሉ አሉ… ይህስ ይሁን።Fake-Indian-degrees-abound

ድህረ ምረቃ ፕሮግራም ላይ መሆኑን አንድም ቀን ሲናገር ሰምታችሁ የማታውቁት በቅርብ የምታውቁት ሰው ፣ እንዲያውም በመደበኛ ትምህርት ከስንተኛ ክፍል ነበር? አቋርጦ ወደ ሄደበት ሄዶ (ጫካ ወይንም ምርኮ) ግን የዛሬ ‘ሹም’ ‘የማስተርስ ፣ ዶክትሬት ዲግሬዬ በፖሰታ ስለደረሰኝ የደስታዬ ተካፋይ እንድትሆን ብሎ ቢጠራችሁስ? ይኼ ሰው ድሮ ትምህርት ቤት የተመዘገበበት ስም ሌላ ነበር… አሁን ደግሞ አዲስ ስም ብቻ ሳይሆን አዲስ ማዕረግ ፣ አዲስ ቤት ፣ አዲስ መኪና… ምኑ ቅጡ… ባናቱ ላይ ዲግሪ ሸምቶበታል።

ይድረስ ለተከበሩ… አስፈላጊውን ክፍያ ስላጠናቀቁ የ ማስተርስ ዲግሪዎን አያይዘን ልከናል – ለዶክተሬት ዲግሪዎ ተመልሰው እንደሚመጡ ተስፋ እናደርጋለን – የዋጋ ቅናሽም እናደርግሎታለን – ስለ ደንበኝነታችን ሲሉ አገልግሎታችንን ለስራ ባልደረቦችዎ እንዲያስተዋውቁልን ትብብሮን እንጠይቃለን – ለዚህም ተገቢውን ወሮታ እንከፍላለን – ያስታውሱ ‘ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ’ – ሴንቸሪ ዩንቨርሲቲ

ታዲያ እርሶም ለምርቃቱ ተጋብዘዋል – በተጠራው ድግስ ላይ ‘…ሁለተኛ ደረጃ ትምህርትህን የት ነበር የጨረስከው ፣ ማትሪክ ውጤትህስ ስንት ነበር ፣ የመጀመሪያው ዲግሪህስ… ያጠናኸው ፣ የተመራመርከው እና መቸ ያዘጋጀኸው መመሪቂያ ቴሲስ ነው ለዚህ ያበቃህ?…’ ብላችሁ ትጠይቃላችሁ ወይስ ድግሱን ተቋድሳችሁ …እንኳን ለዚህ አበቃህ ብላችሁ መርቃችሁ ትመለሳላችሁ?

አነሳስቶ ላስጀመረን ፣ አስጀምሮ ላስጨረሰን ተብሎ ባደባባይ በግልፅ ሳይተያዩ ማስትሬት እና ፒኤችዲ እንደ መለዋወጫ እቃ ‘…ኦን ላይን ኦርደር…’ ማድረግ የወቅቱ የወያኔ ሹማምንት ልዩ መታወቂያ መሆኑን ስናይ ‘ኦ ዲግሪ ሆይ ከስምሽ ጀርባ ስንት ደደብ መሸገ’ እንድንል ያስገድደናል። ባንድ ጀምበር ሚሊየነር ፣ ባንድ ጀምበር ጄነራል እናም ባንድ ጀምበር ዶክተር እገሌ መባል ወያኔአዊ ተፈጥሮ ያመጣብን በሽታ ነው። እነኝህ ሰዎች በየመስኩ በሚፈጥሩት ስፍር ቁጥር የሌለው የተዛባና ህገ ወጥ አሰራር ጉዳቱ ውሎ አድሮ አገሪቱ ላይ በሁለንተናዊ መልኩ እየተንፀባረቀ መሆኑን ለመናገር የሚያስቸግር አይመሰለኝም። አዲሱ ሚሊየነር በሙስና እና ነጠቃ ላይ የተገነባ መሆኑ ፣ ጄነራሉ ችግር ሁሉ የሚፈታው በጠመንጃ ብቻ ነው ሲል የቁጩ ማስተርስ እና ዶክተርም የነሲብ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ መፍትሔ ሲያረቅ ሲያማክር… እንዲያው ተያይዞ ገደል መግባት መሆኑ ቁልጭ ብሎ አይታያችሁም?

‘…ለኢህአዴግ ታማኝ እስከሆነ ድረስ ማይም እንኳ ሚኒስትር መሆን ይችላል…’ ያለው ማን ነበር? ሙት ወቃሽ እንዳልሆን ብዬ እንጂ ይኼ ድኩም ራዕይ የተሰነቀው ገና ከጠዋቱ እንደነበር አትዘንጉ ለማለት ነው። የአሳ ግማቱ ከወደ አናቱ!!

አንኳንስ ዶክተሬት ስምንተኛ ክፍል ሲጨርሱ ካባ ለብሶ ፎቶ መነሳት ፣ የምርቃት ቀን ደግሞ ሽክ ባለ ልብስ ፣ ባጌጠ አደራሽ ፣ ሞቅ ደመቅ ባለ ስነስርዓት ዘመኑን መቋጨት እዚህ በምእራቡ አለም ጭምር የተለመደ ነው። ከዩንቨርሲቲ ሲመረቁ ደግሞ ስርዓቱ ለየት ይላል – ይኼ ሁሉ የሚደረገው ግን አንድም ትምህርት በአግባቡ የተሰጠ ለመሆኑ ይፋዊ ማረጋገጫ ለመስጠት ሲሆን – ሽፍንፍን ፣ ድብቅብቅ ተመርቂያለሁ ማለት ባካዳሚው አለም ሆነ በህብረተሰቡ ውስጥ ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ መሆኑን ለማሳየት ጭምር ነው። ይህን ስል በወያኔ ተቋማት አደባባይ የተመረቀ ሁሉ ብቃቱ ተረጋግጧል ማለቴ አይደለም።

ወያኔ ሁሉንም ዘዴ እንደ አስፈላጊነቱ ይጠቀምበታል። ከገበያ መሸመት ያለባቸው ሹሞች በጀት ተይዞላቸዋል – በተጠረቡ ቤቶች ውለው አድረው ‘የሚመረቁ’ ደግሞ አሉ… ከሲቪል ኢንሲቲትዩት… ከዚህ ሰፈር ከዚያ ሰፈር ኮሌጅ… ከዚህ ከዚያ ህዝቦች ዩንቨርሲቲ… ኮብል ስቶን ጠራቢ ምሩቃን ከታማኝ የወያኔ ካድሬ ምሩቃን ጋር ተማክረው ስለጉዳዩ የበለጠ ሊነግሩን ይችላሉ።

በምዕራቡ የትምህርት አለም ግን ልጆቻችሁን አስተምረን እዚህ አድርሰናል ፣ አዘጋጅተናል ፤ ኑ ተረከቡን የሚል ጥሪ ለወላጆች ሲቀርብ – ወጣቶቹ ለመጪው የከፍተኛ ትምህርት ዘመን ወይንም ለላቀ ሀላፊነት መዘጋጀታቸውን ለማብሰር ብቻ ሳይሆን ጠንክረው በጥሩ ውጤት ያጠናቀቁትን በአርአያነት በአደባባይ በመሸለም ሌሎችም እንዲተጉ ለማበረታታት ጭምር ነው። ይህም የሚደረገው አለምክንያት አይደለም።

የትምህርት ደረጃ የማይዛነፍ ራሱን የቻለ እርከን ፣ አድማስ እና ጥልቀት አለው – በትምህርት ገበታ የተወሰነ አመታት ማሳለፍ በራሱ የተጠና ፣ የተወጠነ ግብአት ያለው መሆኑንም መረዳት አያዳግትም። እያንዳንዱ እርከን ከዕድሜና የአይምሮ መጎልመስ ጋር ተቀናጅቶ ፣ በጥንቃቄ ተመጥኖ እየተለካ ዕውቀት የመመገብ ዘዴ ተዘርግቷል – መደመር እና መቀነስ ብለው ሳይጀምሩ ፣ ረጅሙን የሂሳብ ጎዳና ሳይጓዙ ካልኩለስ ስሌት ውስጥ መግባት እንደማይቻል ሁሉ ወግ ያለው መደበኛ ትምህርት በተገቢው መንገድ ሳይታለፍ ባቋራጭ ማስተርስ እና ፒኤችዲ አገኘሁ ማለት ራስን ከማጃጃል አልፎ ጦሱ የት እየለሌ ነው።

የረባ ዕውቀት ሳይጨብጡ ድሀ አገርን ያህል ለመምራት መድፈር ፣ ‘ድህነትን ታሪክ እናደርጋለን’ ከሚል ባዶ መፈክር የዘለለ ፋይዳ የለውም – ውጤቱ ከባዶ ጣሳ ወደ ተቀደደ ጣሳ ውሀ አገላብጥኩ እንደ ማለት ያህል ነው። ይሄም ባዶ ያም ባዶ – ከባዶ ለባዶ!! Blank of blank ይሉታል ፈረንጆቹ።

በመጀመሪያ ዲግሪ ለመመረቅ አራት ዓመታት የሚፈጀው በሚሰጡት ኮርሶች የሚገኘው ዕውቀት ብቻውን ያን ያህል ዘመን ይፈጃል ተብሎ አይመስለኝም። ተማሪው አራት ዓመታት በዚያ የእውቀት ማዕከል ሲመላለስ ከመደበኛው ትምህርት ሌላ ማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊ ፣ አለም አቀፋዊ እና ቤተሰባዊ ልምድ እና እውቀት አጣምሮ በመቅሰም አይምሮውን ያጎለምሳል። ካንድ ደረጃ ወደሚቀጥለው ለመሻገር የትናንቱ ለዛሬው ፣ የዛሬው ለነገው የሚያወርሱት መሰረት እጅግ አስፈላጊ ናቸው። መደበኛ ትምህርት ወደ ስራ አለም ሲሰማሩ ሀላፊነትን በብቃት ለመወጣት የሚያስችል ስንቅ መደቆሻ አምባ ነው። በወጉ ሳይሰንቁ ሩቅ ለመጓዝ አይታሰብም ፣ በድፍረት የመጣው ይምጣ ብሎ መጓዝ ይቻል ይሆናል ውጤቱ ግን ባዶ መፈክር እያመረቱ ማደናገር ይሆናል – ከባዶ ጭንቅላት የሚመነጩ መፈክሮች መሬት ላይ ካለው ውነት ጋር የሚጣረሱ ለመሆናቸው ያለፉትን 23 ዓመታት ብቻ ማስተዋል ይበቃል – በቀን ሶስት ጊዜ ትበላለህ አይነት!!

ትምህርት እውቀት ነው ፣ እውቀት ደግሞ ሀይል ነው። የትምህርት ማዕረግ ሸምቶ ባልሰለጠኑበት ደረጃ እና ብቃት ሀላፊነት ላይ መቀመጥ ‘ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት ዳገት ላይ ይለግማል’ እንዲሉ ፈታኙን የህብረተሰብ ሁለንተናዊ ችግሮች ለመጋፈጥ እና ለማቃለል ከቶውንም ማጠፊያው ይቸግራል። ይህንነም በተጨባጭ እያየነው ነው – እቅድ ተነደፈ ተብሎ ወረቀት ላይ የሚለቀልቁት ቅዠት ከዕውቀት ማነስ የሚመነጭ መደናበር ነው። በየዘመኑ ማክተሚያ ‘እቅዳችን ያልተሳካው …’ 99 ሰበብ መደርደር።

በቅርቡ ይፋ ሆነው ባነበብናቸው የምርመራ ዘገባዎች እንደተገነዘብነው አገራችን ከቶውንም የዩንቨርሲቲ ደጃፍ መርገጥ ቀርቶ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በወጉ ያላጠናቀቁ ባለስልጣናት የተሸከሙትን የሙያ ማረጋገጫ ምስክር ሰነድ እያየን ነው። ሳይማሩ የጠመጠሙ ዳውላ ሹማምንት እየበረከቱ መሆኑን በማስረጃ ተደግፎ የቀረበው ዘገባ አረጋግጧል። ይኼ ዜና አሳፋሪነቱ ድርጊቱን ለፈፀሙት ቱባ ባለስልጣናት ብቻ ሳይሆን እነዚህን ታቅፎ ተመርኩዞ አገር እየገዛ ላለው የወያኔ ስርአት ጭምር ነው።

ወያኔ ግን ሀፍረት ያውቃል እንዴ?

ይችን አስተያየት ለመክተብ ያነሳሳኝ ዋና ምክንያት ድንቅ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ባቀረበው በዚህ ጥናታዊ ዘገባ ከተጋለጡት (ቅሌት ከተከናነቡት ብል ይሻላል) ግለሰቦች አንዱ አቶ ቆስጠንጢኖስን ባንድ አገጣሚ የማውቀው በመሆኑ ነው። ሰውዬውን ያገኘሁት እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር 1971 – 72 አብረን ማዕከላዊ ብሎም ከርቸሌ በቆየንባቸው የእስር ዘመናት ነበር። ያንን የእስር ዘመን በሚመለከት በቃለ መጠይቅ የተናገረውንም ሰምቻለሁ… ቆስጤ ያው እንደ ጥንቱ ነው – ሲናገር ሳግ አያንቀውም – የሴንቸሪው ዶክተሬት በባህሪው ላይ ለውጥ አላመጣም።

በሰኔ ወር 1971 ዓም በደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢ ደርግን የሚያሰጋ አንዳች ህቡዕ እንቅስቃሴ በደህንነት መስሪያ ቤት የተደረሰበት መሆኑ ይወራል። በዚህ እንቅስቃሴ ተሳትፈዋል የተባሉ አስራ ዘጠኝ ያህል የጂጌሳ እና ሰንቀሌ እንጨት መሰንጠቂያ ወዛደሮች (በደን ልማት ባለስልጣን ስር የነበሩ ፋብሪካዎች ናቸው) የፋብሪካዎቹ ዋና ስራ አስኪያጅ አለማየሁ ዘውዴ እንዲሁም በሻሸመኔ እና አካባቢው በልዩ ልዩ መስክ የተሰማራን ግለሰቦች በአካባቢው የደርግ ተጠሪ ኮሎኔል አባተ መርሻ አዝማችነት ከያለንበት ታድነን ደቡብ ጦር ሰፈር በሚገኝ እስር ቤት ገባን። በማግስቱ በከፍተኛ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች አጀብ አዲስ አበባ ተጓጉዘን ማዕከላዊ እስር ቤት እንታጎራለን። የተከሰስንበት ጉዳይ መንግስትን በወታደራዊ ሀይል ለመገልበጥ ዝግጅት ማድረግ የሚል ነበር። ‘… ጦር መሳሪያ አከማችታችሁዋል ፣ ወታደራዊ ስልጠና እየወሰዳችሁ ነው..’ ይላል የክሱ ቻርጅ። ከታሰርነው መካከል አንድም ወታደር የለም – እርግጥ ነው እሳት ከሌለ ጭስ የለም… እሳቱ ግን የነደደው ሌላ ሩቅ ሩቅ ሰፈር ነበር… ዝርዝሩ ወደ ሌላ ታሪክ ስለሚወስደን ለጊዜው እዘለዋለሁ።

ይህ በንዲህ እንዳለ አዲስ አበባ የደን ልማት ሰራተኞች ማህበር ሊቀመንበር ሀይሉ ዳኜ ተይዞ በኛ የክስ ሰነድ ተካተተ ፤ ብዙም ሳይቆይ ቀንደኛው ተጠርጣሪ ቆስጠንጢኖስ በረኼ ነው በሚል እሱም ተይዞ መጣ።

ቆስጤን በዝና እንጂ እስከዚያ ድረስ በአካል አላውቀውም ነበር… ደን ልማት ውስጥ ማለፊያ ስልጣን ያለው ሰው ሲሆን ተወዳጅ ተክለሰውነትም ነበረው… ረጋ ብሎ መናገር… ግን ሳያቋርጥ የመናገር ችሎታ አለው። ምንም ርዕስ ስጡት ቆስጤ እንደ ልዩ ባለሙያ ይተነትነዋል ፣ ያብራራዋል… ልዩ ተስጥኦ ነው። ታዲያ ከሚናገራቸው ነገሮች ውስጥ አብላጫው መጨበጫ መያዣ የሌለው ነገር ነበር… የቱ ውነት የቱ ውሸት መሆኑን እንኳ ለመለየት ይቸግራል። ያኔ እኔ ገና የ12ኛ ክፍል የህብረተሰብ ትምህርት ተማሪ ስለነበርኩ ቆስጤ የሚተነትነው የፊዚክስ ንድፈ ሀሳብ ሚስጥር ሆኖብኛል። በዚህ የተነሳ በጣም አደንቀዋለሁ – በብዙሀኑ እስረኛ ዘንድ በዚያን ዘመን ማዕከላዊ ከነበሩ ምሁራን እንደ አንዱ ይቆጠር ይከበርም ነበር።

አወይ ማዕከላዊ! እኛ በታሰርንበር ዘመን እስር ቤቱ ተጨናንቆ እና ገንፍሎ ከቤት ውጭ መተላለፊያው ላይ ሰሌን ዘርግተን መተኛት ነበረብን። ማዕከላዊ ስንገባ እነ ጋሼ አሰፋ ጫቦ በጨለማ ቤት እንደታሰሩ ነው ፣ እኔ የደረሰኝ ላይኛው ግቢ 8 ቁጥር ሲሆን ብዙ ሰዎችን የመተዋወቅ ዕድል አጋጥሞኛል። እዚህ አሜሪካ ባለፈው ዓመት ዋይት ሀውስ ተጋብዞ ከፕሬዘደንት ኦባማ ልዩ ክብር የተቸረው ሳይንቲስቱ ዶር ሰለሞን ቢልልኝ የ8 ቁጥር ባልደረባዬ እንደነበረም አስታውሳለሁ።

የቼዝ ጨዋታ ስልት አስተምሮ ለውድድር እንድሰለፍ ያበቃኝ ሙባረክ ሸሪፍ (የሸሪፍ ላውንደሪ ባለቤት ልጅ) ከዚያው ከ8 ቁጥር ነበር ሌሊት ሌላ ክፍል ታስረው ከነበሩ ጓዶቹ ጋር ተወስዶ የተረሸነው (ከብርሀነመስቀል ረዳ ጋር ከጫካ የተያዙ ወጣቶች ናቸው)። እስከዛሬ ድረስ በቤተሰብ ደረጃ ግነኙነታችን ተጠብቆ የሚገኝ የዚያን ጊዜ የ8 ቁጥር እስረኛ ባልደረባዬ በቀለ ተፈራ ዛሬ ከነቤተሰቡ ጀርመን አገር ይኖራል… አዲስ አበባ ታዋቂ ኮማሪቶች ፔጆ 504 ወርቅና ውድ ጌጣ ጌጥ እየሸመተ ሲያንቆጠቁጣቸው የነበረው የመንግስት እርሻ ልማት ሀላፊ የነበረውን በርሔ ተመልሶንስ ታስታውሱታላችሁ? እሱም 8 ቁጥር ነበር። ስንቱ ይነገራል።

አለም በቃኝ ሲወስዱን ደግሞ የልጅነት ጓደኛዬን የሽመልስ ኦላና ታናናሽ ወንድሞች ሀይለልዑል እና ዳኜ አገኘሁዋቸው። ሽመልስ ኦላና አምቦ አካባቢ በግፍ መገደሉ ሳይበቃ ደርግ መላ ቤተሰቡን ለረጅም ጊዜ በእስር አሰቃይቷል ፣ ቤት ንብረታቸውን ቀምቶ ባዶ አስቀርቷቸዋል። አባቱ አንጋፋው ኦቦ ኦላና ባቲ በወያኔ ዘምንም ቢሆን ከመንገላታታት አላመለጡም። አንዳንድ ቤተሰብ ላይ የወረደውን ግፍ ሲያስቡት ይዘገንናል።

ከርቸሌም ቢሆን በየቤቱ ከታጎረው እስረኛ ሌላ አለም በቃኝ ክልል ሜዳው ላይ የላስቲክ ጎጆ ቀይሶ የሚያድረው ቁጥሩ እጅግ ብዙ ነበር። የመጀመሪያ ቀን አዳሬን ያደረኩት የ8 ቁጥር ባልደረባዬ ከነበረው ከመሐመድ ኢዛም ጋር ሲሆን – (መቸም 8 ቁጥር ኖሮ መሀመድ ኢዛምን የሚዘነጋው ያለ አይመስለኝም)። ተናግሮ የሚያስቅ ፣ ፈገግታ ከፊቱ የማይለይ ፣ ጨርሶ እስር ቤት መሆኑን ለመዘንጋት እና ሌሎችም እንዲዘነጉ ለማድረግ የነበረው ተሰጥኦ የሚገርም ነው። የኮሜርስ ምሩቅ እና የባንክ ሰራተኛ ነበር – ታዲያ የዚያን ዕለት ሜዳ ላይ አነጣጥፈን ከመተኛታችን ዝናም መንጠባጠብ ይጀምራል – መጠለያ የሚሉት ነገር የለም ምክንያቱም ቤት ውስጥ የሚተኙት በሙሉ ተቆልፎባቸዋል – መሀል ላይ ያለው በረንዳ ለጠጠር መወርወሪያ የሚሆን ክፍተት አንኳን የለውም – እስረኛው እንደ ርስቱ የሚቆጥረው የመኝታ መደብ አጨናንቆታል። እናማ ከዝናም መሸሻ ቦታ የለም። መሐመድ ኢዛም ግን እንዲህ አለኝ ‘አይዞህ አትስጋ ዝናም በአስማት የማቆም ችሎታ አለኝ… ብቻ የሚሆነውን ጠብቅ’ ሲል በማይገባኝ ቋንቋ መለፍለፍ ጀመረ…. ውነትም አስገምግሞ የመጣው ዝናብ በመንጠባጠብ ቀስ በቀስ በረደ – እኛም አንቀላፋን። ሁዋላ ውጭ ከመተኛት የታደጉኝ የሸመልስ ወንድሞች ናቸው።

ብዙ ትዝታ ያተረፍንበት ዘመን። … ወደ ቆስጤ ልመልሳችሁ።

እንዳልኩት በዚህ ጉዳይ ላይ ለመፃፍ ያነሳሳኝ የቆስጤ ነገር ነው። ትምህርቱን ከአዲስ አበባ ዪንቨርሲቲ ያውም በአፄው ዘመን ያጠናቀቀ ማለፊያ ጭንቅላት የነበረው ቆስጤ ምን ሲያደርግ የዩንቨርሲቲ ደጃፍ ረግጠው ከማያውቁ እነ አባዱላ ገመዳ ተርታ የሚያስልፈው ድርጊት እንደ ፈፀመ ሳስበው ይገርመኛል? በውነቱ በፖለቲካ እምነቱ ከወያኔ ጎን ቢሰለፍ ፣ እሱም እንደነሱ የዘር ሐረግ መዝዞ ይህን እና ያንን ስልጣን ቢጨብጥ ለምን ይህን አደረክ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ላይሆን ይችላል – ሰልጣን በዘር መስፈርት እንደ ቆሎ በሚታደልበት ዘመን እሱም ከዚያ ሰልፍ ውስጥ መግባቱ ቢያስቆጭም ትምህርትን ያክል ታላቅ ነገር የዘረኞች ማላገጫ ሲደረግ ግን ለምን እሱ ራሱ ግንባር ቀደም አድራጊ ፈፃሚ ሆነ? ውሻ በቀደደው…

ቆስጤ ይበልጥ ትዝ የሚለኝ ከርቸሌ ወደኛ ክፍል ተዳብሎ መኖር ከጀመረ በሁዋላ የሆነው አጋጣሚ ነበር። ዘመኑ 1972 ወሩ ትዝ አይለኝም ለሆነ የእስልምና ብሔራዊ በአል ቀን ወህኒ ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ ጫት በይፋ እንዲገባ ይፈቀዳል – በዕለቱ ከውጭ በገባልን ጫት ምርቃና ሞቅ ደመቅ ያለ ውይይት ተከፍቶ ብዙም ሳይቆይ መድረኩ ለቆስጤ ይሰጠዋል። የንግግሩ ርዕስ ስለ ፊዚክስ የትምህርት መስክ ሲሆን በወቅቱ በመስኩ ስለተገኙ አዳዲስ ግኝቶች ምን ሊነግረን እንደሚችል ከቤቱ ጥያቄ ቀረበ። ቆስጤ ትንተናውን ጀመረ – ያኔ እኔ የ12ኛ ክፍል የሶሻል ሳይንስ ተማሪ ስለነበርኩ ስለፊዚክስ ብዙም ዝንባሌ አልነበረኝም። ይሁንና ቆስጤ ከሚሰጠው ትንታኔ በተለይ ስለ ህዋ ምርምር የተደረሰበትን ጭብጥ ሲያብራራ ሁላችንም ፈዘን በተመስጦ ‘በምርቃና’ መንፈስ እንከታተለው ነበር። አገላለፁ ቴክኒካል ተርም የሚበዛበት በመሆኑ ይመስለኛል አብዛኛው ነገር አልገባኝም – ሁላችንም ግን ባድናቆት ተከታትለነዋል። ያን ያህል ራሱን መግለፅ የሚችል ሰው ፣ የመጀመሪያ ዲግሪውን አንቱ ከተባለው የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ለፍቶ ደክሞ ያገኘ ሰው እንዴት መደበኛ ትምህርታቸውን በወጉ እንኳን ካላገባደዱት እነ አባዱላ ገመዳ ተራ ለመሰለፍ መረጠ? መልሱን በጨዋ ደንብ ሊሰጠን የሚችለው ቆስጤ ብቻ ነው።

ዛሬ አለም ያለበትን የቴክኖሎጂ ዕድገት ደረጃ ስናይ የሰውን ዘር ለዚህ ምጥቀት ያበቁ ሳይንቲስቶች በየዘመኑ ተጠበው በምርምር ባስገኙት ውጤት መሆኑ ግልፅ ነው። ከጥንት እስከ አሁን ደረጃ በደረጃ እየበለፀገ እየዳበረ ዕውቀት ይበልጥ እየረቀቅ ብሎም እያንዳንዱ መስክ ዳብሮ ልዩ የሙያ ዘርፍ መፍጠር አስፈላጊ የሆነበት ዘመን ላይ ነን። የስራ ክፍፍል ለብቃት መጎልበት አይነተኛ መሣሪያ እንደሆነ ሁሉ ካንድ የጠቅላላ ዕውቀት ዘርፍ ወደ ሰፔሸላይዜሽን ሽግግር የሚደረገው ያው ብቃትን ለማጎልበት ሲባል ነው። ይኼ ደግሞ በድህረ ምርቃ የትምህርት ዘርፍ ስልጠና እና ምርምር በማድረግ የሚጨበጥ ውጤት ነው። ታዲያ ከምድር ተነስቶ የድህረ ምረቃ ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት መሸመት ባጠቃላይ ባገሪቱ እና በተለይ በትምህርት ገበያ ዘንድ ያለውን ሚዛን ምን ያህል እንደሚያዛባው የሚጠፋው ማነው? ቆስጤ ኦን ላይን ኦርደር የተደረገ ዲግሪ መሸመት ትምህርትን በቁሙ ለመግደል ከተሰለፉ ማይማን ተርታ እንደሚያሰልፈው እንዴት ጠፋው?

አገርን ለመግደል የትምህርት ስርዓቱን መግደል ፣ የትምህርትን ብቃት ዋጋ ማሳጣት እና ስልጣንና ሀላፊነት ዘር መዝዞ ለተጠጋ ሆዳም ማስታቀፍ – ይኼ ነው ከወያኔ አንቀፅ 39 ያተረፍነው – ትምህርት እና በተግባር የተፈተነ የሙያ ብቃት ሳይሆን ከዚህ ከዚያ ዘር መምጣት… እናም ስለ ዲግሪው ሴንቸሪ ዩንቨርሲቲ ይጨነቅበት።

ዶክተሬት በፖሰታ ልኬልሀለሁ
የድሮ ስምህን ደልዠዋለሁ…. አጅሬ ዶክ…

The post ማስተርስ/ዶክተሬት እንደ መለዋወጫ እቃ! (ታሪኩ አባዳማ) appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

አፈረች ዲያቆን –ቀስቶ ወተረ

$
0
0

daniel-kibret-300x207ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በሰባኪነት የታወቀ እንደ ሆነ ይነገርለታል ። በአንድ ወቅት እዚህ አሜሪካ ሳሉ የአሁኑ የአዲስ አበባው መንግሥት ሹመኛ የሆኑ አባ ማርቆስ ፥ ያገለግሉበት ከነበረው ቤተ ክርስቲያን የነበሩ ወጣት ክርስቲያኖች ፥ ዲያቆን ዳንኤል መጥቶ ማስተማር አለበት እያሉ ያስቸግሯቸውና ይጋበዛል ። ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ለማስተማር መዘጋጀቱን እንጂ ከዚያ ያለፈ ነገር አለ ብሎ አላሰበም ። ካህኑ በል ነገ የምታስተምረው አንተ ስለ ሆነክ ፥ ቀደም ብለህ መጥተህ በዲቁና ቀድሰህ ታስተምራለህ ይሉታል ። ዳኒ ትንሽ ያቅማማል ። አሁንም ይጫኑታል አይ ቅዳሴ እንኳን አልችልም ይላል ። በዚህ ጊዜ “አፈረች ዲያቆን” ታዲያ የዲቁና ቅዳሴ ሳትችል በየት አልፈህ አስተማሪ ሆንክ በማለት “አፈረች ዲያቆን” ብለው ተርተውበታል ። -–[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ—–

The post አፈረች ዲያቆን – ቀስቶ ወተረ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

የቴሌቭዥን ድራማዎች በስድስተኛውም የስሜት ህዋሳችንም መቃኘቱን አንርሳ; የትኞቹ ያስተምራሉ? የትኞቹ መታረም ይፈልጋሉ? ”ቤቶች”እና ”ሞጋቾች”ድራማ

$
0
0

Mogachoch
(የጉዳያችን አጭር ማስታወሻ)

ከጌታቸው በቀለ

በቴሌቭዥን የሚተላለፉ መርሐ ግብሮች አነሰም በዛም በሕዝብ ላይ የሚፈጥሩት የእረጅም ጊዜ ተፅኖ ቀላል አይደለም።በተለይ በታዳጊ ወጣቶች እና ልጆች ላይ ለነገ እነርሱነታቸው የሚጭረው ስሜትም ሆነ አለማቸውን እና አካባቢያቸውን የሚመለከቱበት ዕይታ የጠበበ አልያም የሰፋ ወይንም የተንሸዋረረ የመሆን እድሉ ትልቅ ነው።እዚህ ላይ ወላጆች ለልጆቻቸው ከቴሌቭዥን መርሃ ግብር በኃላ የሚሰጡት የማስተካከያ ሃሳብ ወይንም ልጆችም ሆኑ ወጣቶች ጉዳዩን የሚያዩበትን እይታ ቀላል አይደለም።

የኢትዮጵያ ተለቭዥንን በሀገር ውስጥ የመረጃ ምንጭነት ተአማኒነቱ የወረደበትን ደረጃ ለመግለፅ ህዝቡ ”የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን እውነት የምናገረው ሰዓት ብቻ ነው” የሚለውን አባባል መግለፁ ብቻ በቂ ነው።ከግማሽ ክ/ዘመን በላይ በመገናኛ ብዙሃንነት የቆየ የቴሌቭዥን ጣብያ በእዚህ አይነት ደረጃ የወረደ የመረጃ ምንጭ መሆኑ እንደ ኢትዮጵያዊነት በጣም ያሳዝና።ዛሬ ቢልልን ኖሮ ኢቲቪ በመላው ዓለም ባሉ ከተሞች ወኪሎች በኖሩት እና በቀጥታ የሚዘግቡ ዘጋቢዎች በኖሩት ነበር። ይህ ደግሞ ከወጭም አንፃር ብዙ አለነበረም።ምክንያቱም በመላው ዓለም እንደመበተናችን በነፃ አገልግሎት ለመስጠት ፈቃደኛ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ማግኘት ከባድ አይደለም።ነገር ግን አለመታደል ሆኖ አምባገንነት፣ጎሰኝነት እና ሙስና መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደጠረነፈ ሁሉ የኢትዮጵያ ቴሌቭዝንም አንዱ ሰለባ ነው።ኢትዮጵያውያን ግን በሀገር ቤት የታፈነ ድምፃቸውን በቸልታ አላዩትም።በጥቂቶች አስተባባሪነት የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን በመላው ዓለም እና በሀገር ቤት ላሉ ወገኖቻችን ብቸኛው ነፃ የመገናኛ ብዙሃን ለመሆን በቅቷል።

የእዚህ አጭር ማስታወሻ አላማ ስለ ኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ታሪክ ለማውራት አይደለም።ስለሚያቀርባቸው ሳምንታዊ ድራማዎች ግን ትንሽ ማለት ፈለኩ።የቴሌቭዥን ድራማዎቹን ምግብ እየበላሁም ሆነ መንገድ ላይ ባለኝ ክፍት ጊዜ እመለከታቸዋለሁ።ይህንን የማደርገው መዝናኛ ስለሆኑ ብቻ ሳይሆን አሁን ያለውን የሀገር ቤትን ማኅበራዊ፣ስነ-ልቦናዊ፣ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ሁኔታ ስለሚያንፀባርቁልኝ ነው።የድራማዎቹን የመሃል እንቡጥ መልእክት ፈልፍላችሁ ለማግኘት ስትሞክሩ (በስድስተኛው የስሜት ህዋስ ማለቴ ነው) ብዙ ጠቃሚ እና ጎጂ ጎኖቹን ለማየት አያስቸግራችሁም።
በስድስተኛው የስሜት ህዋስ የሶስቱ ድራማዎች እይታ

እዚህ ላይ በቴሌቭዥን ከሚቀርቡት ድራማዎች ውስጥ የሁለቱ ማለትም ”ቤቶች” እና ”ሞጋቾች” ላይ የማነሰው የጠለቀ ሂስ አለመሆኑን እና ያንን ለማድረግ የሙያው ክህሎት እንደሌለኝ ለመግለፅ እፈልጋለሁ።ነገር ግን ድራማዎቹ በህብረተሰባችን ላይ ያላቸው አሉታዊ እና በጎ ተፅኖ ላይ ሃሳብ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
1/ ”ቤቶች” ድራማ

ይህ በየሳምንቱ ቅዳሜ ምሽት የሚቀርበው ድራማ በብዙዎች ዘንድ በአስቂኝነቱ የሚጠቀስ እና በርካታ ተመልካች ያለው መሆኑ ይታወቃል።አመታዊ ዝግጅቱን ሲያዘጋጅም የሚመለከቱት ተመልካቾች በርካታ መሆናቸውን ያሳያል።እንደ እኔ አስተያየት ድራማው ከማዝናናት ባለፈ ሊያስተምር የሚገባው በርካታ ነገሮች ይቀሩታል።በመጀመርያ ደረጃ ታሪኩ አንድ በግንብ በታጠረ ቪላ ቤት ውስጥ የሚኖር ቤተሰብ ዙርያ ያጠነጥናል።ቤተሰቡን መካከለኛ ገቢ ያለው ቤተሰብ ለማለት ይከብደኛል።ምክንያቱም መካከለኛ ገቢ የሚባለው ሕብረተሰብ አሁን በራሱ ጠፍቷል።ከሃያ ሶስት አመታት በፊት አንድ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር መሬት ተመርቶ ቤት የመስራት አቅም ነበረው።ዛሬ ቤት ለመስራት ከፍተኛ ገቢ ካላቸው ውስጥ የሚመደብ ካልሆነ አይታሰብም።እናም ድራማው ውስጥ የሚተውኑት ቤተሰብ አባላት ቢያንስ ባለ ሁለት ሰራተኛ እና አንድ የጥበቃ ግለሰብ የሚተዳደሩ ናቸው እና መካከለኛ ከሚለው እናውጣቸው።እዚህ ላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከ95% በላይ በእንደዚህ አይነት ኑሮ የሚኖር አይደለም።አዲስ አበባ ብቻ የግል መፀዳጃ የሌለው የሕዝብ ብዛት ከ70% በላይ እንደሆነ ከተገለጠ እሩቅ አይደለም።በመሆኑም ድራማው ተጨባጩን የሀገራችንን ሕዝብ ኑሮ አይወክልም።ይህ ግን ድራማውን ያስወቅሰዋል እያልኩ አይደለም።ጥቂቶችም ብዙሃኑ ግብር በሚከፍልበት ቴሌቭዥን እርስ በርስ ሲጨዋወቱ መመልከት በራሱ ድራማ ነውና።
Tilahun Gugsa
በእዚህ ድራማ ላይ ”ይቤ” ገፀ ባህሪ ይዞ የሚጫወተው ወጣት የዩንቨርስቲ ተማሪ ለወጣቱ ምን ያስተምራል? ብዬ ስጠይቅ በገፀ ባህሩ ላይ ባብዛኛው አሁን በዘመነ ኢህአዲግ/ወያኔ አንድ የዩንቨርስቲ ተማሪ የሚኖረውን መልክ ይዞ ታገኙታላችሁ።ይቤ በድራማው ላይ ይጠጣል፣ይቅማል፣የተለያዩ የሴት ወዳጆች አሉት፣የሚናገረው የተደበላለቀ ማለትም ”ከአራዳ አነጋገር” እስከ እንግሊዝኛ የተደባለቁ፣ኢትዮጵያዊነት በሙሉ የጠፉበት ሆኖ እናገኘዋለን።በነገራችን ላይ ይቤ መሃንዲስ ነው እና የነገ ኢንጅነሮቻችን የሚቅሙ፣የሚያጨሱ ናቸው በመሆኑም መስርያቤቶች ከመሃንድሶች ጋር ሲሰበሰቡ የጫት በጀት መያዝ አለባቸው ማለት ነው።

ቤቶች ድራማ ሶስት መስተካከል ነበረባቸው የምላቸው አቀራረብ አይቼበታለሁ

የመጀመርያው በቅርቡ የታየው ነው ታሪኩ እንዲህ ነው።ሁለቱ የቤት ሰራተኞች ቡና እያፈሉ ሳሉ የቤት ጠባቂው ዘበኛ ያገኘውን ዱቄት መሰል ነገር ፍሙ ላይ ሲጨምሩት እና በቤቱ ውስጥ የነበሩት በሙሉ ሲሰክሩ ያሳያል።እንደ ድራማው አገላለፅ ለካ የጨሰው አደገኛ ዕፅ ነበር።ሙሉ ድራማው በወቅቱ ቀጥሎ ያሳየን ነገር ቢኖር አንድ እፅ የወሰደ ሰው ምን እንደሚታየው፣ለምሳሌ ድመት ዘንዶ እንደሚመስለው፣ሰዎች ትልቅ ሆነው እንደምታዩት በተግባር እያሳየ ትውልዱን አሰለጠነ።የሚገርመው ድራማው የእፅን አስከፊነት ሳይሆን አዝናኝነት ነው እስኪበቃን የነገረን።እፅ ያጨሱት በፖሊስ ሲያዙ እና ሲቀጡ ሳይሆን የአደገኛ እፅን አዝናኝነት ለታዳጊ ወጣት ሁሉ ተነገረው።ይህንን የተመለከተ ወጣት ”አንድ ቀን ልሞክረው” እንዲል አድረገው አቀረቡለት።ይህ ክፍል ከታየ ገና ወራት አልተቆተሩም።በአድዋ በዓል ላይ ሸለላችሁ ብሎ ያገደ ፖሊስ ያለው መንግስት በተለቭዝኑ የእፅ አወሳሰድ ስልጠና ሲሰጥ ማየት ያሳምማል።

ሁለተኛው፣ ቤተሰቡ ለሽርሽር ከሄደባቸው ቦታዎች አንዱ ቅዱስ ላሊበላን ያሳየናል።በቅዱስ ላሊበላ ቅፅር ውስጥ በአካል ቤተሰቡ ቆሞ የሚሰጠውን ገለፃ ያዳምጣል።በእምነት ቦታ በመሰረቱ የቀልድ ድራማ መስራት አስቸጋሪ ነው።ድራማው ላይ ግን ሃይማኖታውም ሆነ ታሪካዊ ገለፃ ሲሰጥ በመሃል የፌዝ እና የቀልድ ንግግሮች ይሰሙ ነበር።ይህ እንግዲህ በመሃል ከሚገባው የሳቅ ጋጋታ ጋር አብሮ ነው።የእምነት ቦታዎች የሚሰጣቸው ቦታ እና በአማኙ ዘንድም ሆነ በታዳጊ እና ወጣቶች ዘንድ የሚያሳድረው ተፅኖ ፈፅሞ አልተጤነም።ቅዱስ ላሊበላ ከመጎብኘቱ ባለፈ የከበረ ቀልድ የማይነገርበት ቦታ መሆኑን ማሰብ ተገቢ ነበር።በሌላ በኩል ግን የድራማው አላማ ሀገርህን እወቅ በሁሉም ቤተሰብ መለመድ አለበት የሚለውን ሃሳብ በማንፀባረቁ የሚደገፍ አይደለም እያልኩ አይደለም።ለእምነት ቦታዎች የማይባሉ ቀልዶች ቀላቀለበት እንጂ።

ሶስተኛው የድራማው አቀራረብ የገጠሩን የሀገራችንን ገበሬ ለከተማው ወጣት የሚስልበት የተሳሳተ አቀራረብ ነው።የቤቱ ዘበኛ ሁል ጊዜ እንቅልፍ በጣም ወዳጅ፣ምግብ የሚወድ፣ሥራ የማይወድ እና ግዴለሽ አድርጎ የሚስልበት ገፀ ባህሪ የኢትዮጵያን ገበሬ ፈፅሞ አይወክልም።የኢትዮጵያ ገበሬ እንቅልፍ የለውም ከማለዳ እስከ ምሽት ሲለፋ ውሎ ማታ የቀረውን ሥራ በመስራት የሚጠመድ፣ንቁ፣በሥራ የሚያምን፣ላመነበት የሚሞት እና ለወዳጁ ሟች ነው።ይህንን የህብረተሰብ ክፍል ነው እንግዲህ ለሕዝቡ ”ሎሽ ማለት ብቻ የሚወድ” ተብሎ የሚቀርበው።ይህ በእራሱ ከቀልድ ባለፈ ብዙ ማህበራዊ ነገሮችን የሚነካ ነው።በኮሜዲ ፊልሞች ላይ ገፀ ባህርያት የተለያዩ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖችን እያነሱ ያስተምራሉ እንጂ በኢትዮጵያ ገበሬ ላይ የሚሳለቅ አቀራረብ ይዘው እና ከገበሬው የምንማረው እንቅልፍ ብቻ የመሰለ አቀራረብ ማንንም አይጠቅምም።

እዚህ ላይ የቤቶች ድራማን አንዳንድ ግድፈቶች እና ማስተካከል የሚገባቸውን አቀራረቦች ላይ ሃሳብ ለመስጠት ፍለግሁ እንጂ በደፈናው ድራማውን ለማጣጣል እንዳልተነሳሁ ይታወቅልኝ።ድራማ ከአዝናኝነቱ ባለፈ ወጣቶችን በስነ-ምግባር፣በሀገር ፍቅር ስሜት እና በቅን ለሀገር መስራትን የሚያስተምር ካልሆነ በሳቅ ማንከትከትን ብቻ አላማዬ ብሎ ከተነሳ ስለ እፅ አወሳሰድ የሚያሰለጥነን ከሆነ አደገኛ ነው።ላሰምርበት የምፈልገው ለሕዝብ የሚቀርቡ ድራማዎች በተለያየ ሙያ ላይ ያሉ አማካሪዎች ያስፈልጋቸዋል።ደራሲው ”ህዝብን ካሳቀ እና መንግስትን እስካላሳቀቀ ድረስ መንገዱ ሰላም ነው” በሚል አስተሳሰብ ብቻ አየር ላይ ማዋል የለበትም።

”ሞጋቾች” ድራማ

ከእዚህ በአንፃሩ በ”ኢቢኤስ”ቴሌቭዥን የሚቀርበው ”ሞጋቾች” የተሰኘው ድራማ ጥሩ፣አስተማሪ እና ትውልድን የሚያንፅ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።ሞጋቾች በአንድ ሆስፒታል ውስጥ የሚሰሩ የህክምና ዶክተሮች እንዴት ህዝባቸውን በታማኝነት እንደሚያገለግሉ እና በማህበራዊ ኑሮአቸው ውስጥ የሚገጥማቸውን ተግዳሮት ያሳያል።የሞጋቾች ድራማ በፊልም አቀራረፅ እና የድምፅ ጥራቱ ብቻ ሳይሆን የመረጡት ሆስፒታል ተራው ሕዝብ የሚገለገልበትን እና እታች ያለው ሕዝብ የሚላቸውን አባባሎች፣ስሜቶችን ሁሉ የሚያንፀባርቅ አቀራረብ ይታይበታል።እዚህ ላይ ማስታወሻዬ አጭር ከመሆኑ አንፃር ባጭሩ ”ሞጋቾች”ድራማ ሶስት ነገሮችን ለአዲሱ ትውልድ እንደሚያስተምር ጠቅሼ ሃሳቤን ልግታ።

1/ ተምሮ በሀገር መስራትን እና ወገንን ማገልገልን
በድራማው ብዙ ክፍሎች ላይ የሚታዩት አቀራረቦች በዶክተር ደረጃ ያሉ የህክምና ባለሙያዎች ምን ያህል እታች ላለው ሕዝብ እንደሚጨነቁ እና ኃላፊነት እንደሚሰማቸው ያሳያል።

2/ የዩንቨርስቲ ሴት ተማሪዎች ጥንቁቅ እንዲሆኑ ይመክራል
የድራማው ዋና ገፀ ባህሪ በአንድ ወቅት የዩንቨርስቲ ተማሪ ሆና ሳላ አንድ ምሽት በተፈጠረ የምሽት ዳንስ ይመሽባትና ከሰው ቤት ታድራለች።ሆኖም በእዚችው ምሽት ተደፍራ ልጅ ትወልዳለች።ድራማው ባብዛኛው የወለደቻትን ልጅ አባት በመፈለግ ስትደክም ያሳያል።ይህ አሁን ላሉት ወጣቶች እያንዳንዱ ምሽት የምትሰራ ስህተት እና ከዋልጌ ተማሪዎች ጋር መግጠም የሚያስከፍለው ዋጋ ለአመታት የሚተርፍ መሆኑን ያሳያል።ይህም በተለይ ሴት ወጣቶች ጥንቁቅ እንዲሆኑ ይመክራል።

3/ በአንድ ወቅት ችግር ቢያጋጥምም መልሶ መነሳት እንደሚቻል ያስተምራል
የድራማው ዋና ገፀ ባህሪ ባንድ ወቅት ተደፍራ ልጅ ለመውለድ ተገደደች።ሆኖም ተመልሳ ጠንክራ በመማሯ ዛሬ ለህክምና ዶክተርነት በቃች።ይህ በራሱ የሚያስተምረው ትምህርት አለ።ወጣቶች ስህተት ላይ ሊወድቁ ይችላሉ ግን ከስህተታቸው ተመልሰው እንደገና ተነስቶ ለቁም ነገር መብቃት ነው ዋናው ቁም ነገር ይለናል የድራማው መልእክት።

ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ድራማዎች የረቀቀ የፕሮፓጋንዳ መስርያ አውድማ ወይንም የተበላሸ ትውልድ ማፍርያ ማሽን እንዳይሆኑ በስድስተኛውም የስሜት ህዋሳችንም መቃኘቱን አንርሳ።

ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
የካቲት 26/2007 ዓም (ማርች 5/2015)

The post የቴሌቭዥን ድራማዎች በስድስተኛውም የስሜት ህዋሳችንም መቃኘቱን አንርሳ; የትኞቹ ያስተምራሉ? የትኞቹ መታረም ይፈልጋሉ? ”ቤቶች” እና ”ሞጋቾች” ድራማ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ሰበር ዜና – የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እየተቃጠለ ነው…

$
0
0

11043009_840026152723491_4165333039653038088_n

ብርቅዬውና በሀገራችን ከሚገኙ ብሄራዊ ፓርኮች አንዱ የሆነው የባሌ ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ እየተቃጠለ ነው፡፡ …

በደን ሀብቱ የሚታወቀው ይህ ፓርክ በተለይም ሼደን፡ ጡርጡራ፣ ቶዮ፣ ቴክአመሌና አበልጣሲም አካባቢዎች እሳቱ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰባቸው ካሉ አካባቢዎች ይጠቀሳሉ፡፡

በእሳቱ በከፍተኛ ደረጃ ጉዳት እየደረሰበት ያለው የአስታ ተክል በኢትዮጵያ ብቻ የምትገኘውን የቆቅ ዝርያ ጨምሮ በርካታ እንስሳትን ያስጠለለ ነው፡፡እሳቱ ዛሬም ለሶስተኛ ቀን መንደዱን ቀጥሏል፡፡ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የፓርኩ ባለሙያዎች እሳቱን ለማቆም እየታገሉ ነው፡፡

The post ሰበር ዜና – የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እየተቃጠለ ነው… appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

በአዋሳ በተማሪዎች ላይ የሕወሃት ሰራዊት ተኩስ እንደከፈተ ተዘገበ

$
0
0

Hawasa University
የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት እንደዘገበው:-

በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ካምፓስ ዉስጥ የሕወሃት ታጣቂዎች በተማሪዎች ላይ ተኩስ እንደከፈቱ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል። በዩኒቨርሲቲ ዛሬ ትምህርት ያልነበረ ሲሆን፣ በርካታ ፌዴራል ፖሊሶች ካምፓሱን ተቆጣጥረዉታል። ጩኸትና ረብሻም ተሰምቷል።

የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች በገጠማቸው የውሀ እጥረት ምክንያት ሲሆን ረብሽ ያነሱት፣ በካምፓስ ዉስጥም ከፍተኛ ግርግር ጩኸትና ተኩስ እንደነበር ታውቋል። በግርግሩም ተማሪዎች እንደተጉዱ በርካታ የፌድራል ፖሊሶች የዩኒቨርሲቲውን ግቢ እንደ ወረሩት ተማሪዎቹንም እየደበደቡና እያፈሱ ወደተለያየ እስር ቤቶች እንደወሰዷቸው ታውቋል ፡፡

ተማሪዎቹ እንደሚሉት ለበርካታ ቀናት ውሀ አጥተው መቸገራቸውን ይህንንም ጉዳይ ለትምህርት ቤቱ ሀላፊዎች ማመልከታቸውን ነገር ግን ችግሩን ሊፈቱላቸው እንዳልቻሉ ተናገረዋል፡፤ ተያይዞም በአከባቢው የሚገኙ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ተማሪዎቹን በመደገፍ አመፁን መቀላቀላቸው ተነገሯል፡፡ አሁን ግርግሩ ቀዝቀዝ ያለ ሲሆን በርካታ የፌድራል ፖሊስ አባላት ከግቢው ውጭ ቆመው ይገኛሉ፡፡

The post በአዋሳ በተማሪዎች ላይ የሕወሃት ሰራዊት ተኩስ እንደከፈተ ተዘገበ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

Sport: ኤፍ ኤ ካፕ 6ኛው ዙር: ማን.ዩናይትድ ከአርሰናል (ልዩ ትንታኔ ስለ ፍልሚያው)

$
0
0

በየሳምንቱ በመላው ዓለም የሚገኙ ስፖርት አፍቃሪያን በጉጉት የሚጠብቁት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በዚህ ሳምንት በኤፍ ኤ ካፕ 6ኛ ዙር ውድድር ተተክቷል፡፡ በእንግሊዝ እግር ኳስ ማህበር (ኤፍ ኤ) አዘጋጅነት ከሚደረጉ የሀገር ውስጥ ውድድሮች ከፕሪሚየር ሊጉ ቀጥሎ ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው የኤፍ ኤ ካፕ ውድድር በርካታ ክለቦችን ጥሎ ስድስተኛ ዙር ላይ ደርሷል፡፡ በስድስተኛው ዙር የኤፍ ኤ ካፕ ውድድር አራት ጨዋታዎች በተለያዩ የእንግሊዝ ከተሞች ይካሄዳሉ፡፡
FA Cup Final 2015
የመጀመሪያው ጨዋታ ቅዳሜ በእንግሊዞች የምሳ ሰዓት ጨዋታ 9፡45 ላይ የሊግ አንዱ ተወዳዳሪ ብራድፎርድ ሲቲ የሻምፒዮንሺፑን ሬዲንግ በሜዳውና በደጋፊው ፊት በሚፋለምበት መርሐ ግብር ይጀመራል፡፡

ብራድፎርድ ሲቲ በሊግ አንድ ውስጥ በ48 ነጥብ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ተጋጣሚው ሬዲንግ በበኩሉ በሻምፒዮንሺፑ በ41 ነጥብ በአሥራ ስምንተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡ የሊግ አንድ የደረጃ ሰንጠረዥን ብሪስቶል ሲቲ በ73 ነጥብ፣ ፕሪስተን በ63 ነጥብ እና ማክዶንስ በ62 ነጥብ ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ያለውን ይዘዋል። የሻምፒ ዮንሺፑን የደረጃ ሰንጠረዥ ደግሞ ሚድል ስቦሮው በ66 ነጥብ፣ ደርቢ ካውንቲ በ65 ነጥብ እንዲሁም ዋትፎርድ በግብ ተቀድሞ በተመሳሳይ 65 ነጥብ ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ በሚቀጥለው ዓመት ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ለማደግ የሚደረገውን ሩጫ እያገባደዱ ይገኛሉ፡፡ ሁለቱ ክለቦች ለስድስተኛ ዙር ጨዋታ የደረሱት ብራድፎርድ ሲቲ ቼልሲና ሰንደርላንድ ጥለው ሲሆን፤ ሬዲንግ በበኩሉ ካርዲፍ ሲቲንና ደርቢ ካውንቲን በጥሎ ማለፍ አሸንፎ መሆኑ ይታወሳል፡፡

ጨዋታው ቀጥሎ ምሽት 2፡30 ላይ አስቶንቪላ በሜዳው ቪላ ፓርክ ላይ ዌስትብሮሚች አልቪዮንን ይገጥማል፡፡ ይህ ጨዋታ ሁለቱ ክለቦች ባለፈው ማክሰኞ በቪላ ፓርክ በ28ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በተገናኙ ሳምንት ሳይሞላቸው ለሁለተኛ ጊዜ የሚገናኙበት ጨዋታ ይሆናል፡፡ አስቶንቪላዎች የቀድሞ አሠልጣኛቸውን ፖል ላምበርትን አባረው በምትኩ የቶትንሃም ሆትስፐር ዋና አሠልጣኝ የነበሩትን ቲም ሽሩድን በአሠልጣኝነት ከቀጠሩ በኋላ መጠነኛ የሚባል ለውጥ ያመጡ ሲሆን፤ ሽሩድም የመጀመሪያ ሦስት ነጥባቸውን አግኘተዋል፡፡ ባለፈው ማክሰኞ የቶኒ ፑሊሱን ዌስትብሮሚች አልቪዮን አስተናግደው ምስጋና ለዳኛው ይግባውና በባከነ ሰዓት በተሰጣቸው የፍጹም ቅጣት ምት ማሸነፋቸው እና የመጀመሪያ ሦስት ነጥባቸውን ማግኘታቸው ከፍተኛ መነሳሳት ፈጥሮላቸዋል፡፡ ዌስትብሮሚች አልቪዮኖች በበኩላቸው በከፍተኛ ግብ አስቆጣሪያቸው በራሂኖ ታግዘው ከፍተኛ የፕሪሜር ሊጉን ሽንፈታቸውን ለመበቀል ወደ ሜዳ እንደሚገቡ ይጠበቃል፡፡

መርሐ ግብሩ ዕሁድ ቀጥሎ ምሽት 1፡00 ላይ የመርሲሳይዱ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ስታዲየም የሻምፒዮን ሺፑን ብላክበረን ሮቨርስን ያስተናግዳል፡፡ ሊቨርፑሎች በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጓቸው ተከታታይ ጨዋታዎች በማሸነፍ ከነበሩበት የ12ኛ ደረጃ ወደ አምስተኛ ደረጃ መምጣታቸው እና ይህንን ጨዋታ በሜዳቸው የሚያደርጉ መሆኑ ከፍተኛ የማሸነፍ ዕድል ተሰጥቶታል፡፡ ብላክበርን በበኩሉ አሁን ያለበት ደረጃ ሊቨርፑልን ሙሉ ለሙሉ ማቆም የሚያስችል ባይሆንም ለጨዋታው ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው በመግባት ለሊቨርፑል ከፍተኛ ፈተና እንደሚሆኑባቸው ይጠበቃል፡፡

አራተኛውና በጉጉት የሚጠበቀው የመጨረሻው ጨዋታ ሰኞ ምሽት 4፡45 ማንቸስተር ዩናይትድንና አርሰናልን ያገናኘው ጨዋታ ነው፡፡ ሁለቱ ክለቦች በተገናኙ ቁጥር ከጨዋታው በላይ በአሠልጣኞችና በተጫዋቾች መካከል የሚደረገው እሰጥ አገባ ሁሌም የሚናፈቅ ነው፡፡ በዚህ ዓመት ደግሞ አርሰናል ከተፋላሚው ማንችስተር ዩናይትድ በፕሪሚየር ሊጉ በአንድ ነጥብ ከፍ ብሎ በሦስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ሲሆን፤ ማንችስተር ዩናይትድ በበኩሉ ከአርሰናል በመቀጠል በአራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ እንደሚታወሳው ሁለቱም ክለቦች ባለፈው ረቡዕ በፕሪሚየር ሊጉ ከሜዳቸው ውጪ ያደረጓቸውን ጨዋታዎች በድል ተወጥተዋል፡፡ ማንችስተር ወደ ጄምስ ፓርክ ስታዲየም አቅንቶ ኒውካስል ዩናይትድን ገጥሞ በ89ኛው ደቂቃ በኒውካስትሉ ግብ ጠባቂ ቲም ክሩል ስህተት ተጠቅሞ አሽሊ ያንግ ባስቆጠራት ግብ 1ለ0 ሲያሸንፍ አርሰናል በበኩሉ ወደ ሎፍተስ ሮድ በማቅናት ኪውፒአርን ገጥሞ ኦሊቬ ጅሩድና አሌክሲስ ሳንቼዝ ባስቆጠሯቸው ሁለት ተከታታይ ግቦች 2ለ1 አሸንፎ መመለሱ አይዘነጋም፡፡

በአራት የተለያዩ ጨዋታዎች ቀጥሎ የሚውለው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ 6ኛ ዙር ውድድር አራት ክለቦችን ወደ ግማሽ ፍጻሜ ሲያሳልፍ አራት ክለቦችን በማሰናበት ይቋጫል፡፡ የፍጻሜው ውድድር በመጪው ግንቦት መጀመሪያ አካባቢ በታላቁ ዌምብሌይ ስታዲየም የሚካሄድ መሆኑ ታውቋል፡፡

The post Sport: ኤፍ ኤ ካፕ 6ኛው ዙር: ማን.ዩናይትድ ከአርሰናል (ልዩ ትንታኔ ስለ ፍልሚያው) appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

Health: የጥብስ ቅጠል የጤና ጥቅሞች Health Benefits of Rosemary

$
0
0

Rosemary
(በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር)
✔ ካንሰርን ይከላከላል
ሮዝመሪ(የጥብስ ቅጠል) በውስጡ የያዘው ካርኖሶል የተባለ ንጥረ ነገር ካንሰርን የመከላከል አቅም እንዳለው ጥናቶች ያሳያሉ፡፡
✔ የማስታወስ ችሎታን ይጨምራል
ከጥንት ጀምሮ ስለዚህ ጥቅሙ የሚነገርለት የጥብስ ቅጠል በውስጡ የያዘዉ ካርኖሲክ አሲድ የአንጎል ነርቮችን የመጠበቅ አቅም ስላለው በህመም ወይም ከእድሜ ጋር በተያያዘ ምክንያት ለሚመጣ የመርሳት ችግር እንዳንጋለጥ ይረዳል፡፡
✔ የማይግሬን ህመምን ያስታግሳል
የጥብስ ቅጠልን በሞቀ ውሃ ዉስጥ በመጨመር ለ 10 ደቂቃ መታጠን ማይግሬን ህመምን ያስታግሳል፡፡
✔ የፀረ ባክቴሪያነት ጥቅም
ጥናቶች እንደሚያሣዩት ከሆነ የጥብስ ቅጠል እንደ ጨጓራ ባክቴሪያ (H. pylori) እና ሌሎችንም ይዋጋል፡፡
✔ የአፍ ጠረንን ለማስወገድ
የጥብስ ቅጠል ተፈጥሮአዊ የሆነ የአፍ ጠረን ማስወገጃ ነዉ። ትንሽ የጥብስ ቅጠልን በሞቀ ዉሃ ዉስጥ አድርጎ መጉመጥመጥ መጥፎ ጠረንን ያስወግዳል።
✔ የቆዳ መሸብሸብን ይከላከላል
የጥብስ ቅጠል በተለያዩ የቆዳ ማለስለሻ ክሬሞች ዉስጥ የሚገባ ሲሆን ቆዳን እንዳየሸበሸብ እና ጤናማ እንዲሆን ይረዳል።
✔ በሽታን የመከላከል አቅምን ያዳብራል
የጥብስ ቅጠል በዉስጡ ያለዉ አንቲ ኦክሲደንት፣ አንቲ ኢንፍላማቶሪ እና አንቲ ካርሲኖጄኒክ ንጥረ ነገር የሰዉነታችንን በሽታ የመከላከል አቅምን እንዲዳብር ይረዳል።
በአብዛኛው ጠቀሜታዉ የሚያመዝነው የጥብስ ቅጠል ነፍሰጡር ሴቶች እና የደም ግፊት ያለባቸው ሰዎች ግን በብዛት እንዲወስዱ አይመከርም።
ጤና ይስጥልኝ

The post Health: የጥብስ ቅጠል የጤና ጥቅሞች Health Benefits of Rosemary appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ያሬድ ጥበቡ ይናገራሉ: የኢትዮጵያ አየር መንገድ 85% የሚቀጥረው ትግሬዎችን ነው * አዲሱ ለገሰ ይህን ተቃውመው የቦርድ ሊቀመንበርነቱን ለቀዋል…ሌሎችም

$
0
0

Yared Tibebu zehabeha

(ዘ-ሐበሻ) የቀድሞው የኢህዴን ታጋይ ጌታቸው ጀቤሳ (ያሬድ ጥበቡ) በፌስቡክ ገጻቸው በጻፉት መረጃ አዳዲስ የኢትዮጵያ አየር መንገድን እና የብአዴንን ገመናዎች ለሕዝብ ይፋ አድርገዋል:: ይህ የአቶ ጌታቸው ጀቤሳ (ያሬድ ጥበቡ) ወቅታዊ መረጃ ከአቶ መለስ በኋላ በተለይ ሕወሓት በኢህ አዴግ ውስጥ ነጥሮ ለመውጣት እያደረገ ያለውን ሴራ ያጋለጠ በመሆኑ በፌስቡክ ገጻቸው ያቀረቡትን ዘ-ሐበሻ እንደወረደ እንደሚከተለው አስተናግዳዋለች::

ከቤተ መፃህፍቴ መስኮት ውጪ የማርች አቦ ጥጥ በረዶ ይነሰነሳል ። ጎረቤቴ ውሻዋን ለማናፈስ ወጥታለች ። እኔ እንኳንስ የውጪውን በረዶ የውስጤንም መቋቋሙ ከብዶኛል ። ውስጤን የበረደኝ ያለምክንያት አይደለም ። ትናንትና ማታ አዲስ ከተሰደዱ ወጣቶች ጋር በሲልቨር ስፕሪንጉ የሉሲ ሬስቶራንት ራት እየበላን ሳለ፣ በኢትዮጵያ አየርመንገድ ውስጥ እየተከናወነው ስላለው ዘረኝነት የሰማሁት እንቅልፍ ነስቶኝ አደረ ። እንቅልፍ ባጣ፣ በዚያውም የሰማሁትን ከማምናቸው ምንጮች ለማጣራት፣ ባህርዳር ደውዬ ሃሎ አልኩ ። ማታ የሰማሁትንም አረጋገጥኩ ። ከመለስ ሞት ወዲህ እየተጠናከረ በመጣው የወያኔ ዘረኝነት የተነሳ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 85 በመቶ የሚቀጥረው ትግሬዎችን ብቻ መደረጉንና ፣ ይህንንም የአቶ ተወልደ ወያኔያዊ እርምጃ በመቃወም አዲሱ ለገሰ ከቦርድ ሊቀመንበርነት መልቀቁንና በቦታውም አባዱላ መተካቱ ተነገረኝ ።

ይህ ለምን አስፈለገ? ለሚለው ጥያቄዬም፣ ከመለስ ሞት ወዲህ ላደረባቸው የበታችነት ስሜትና ፍርሃት፣ አማራጭ አድርገው የወሰዱት ወያኔን እንደ ድርጅት ማጠናከር ፣ ከድርጅቱ ተባረው የነበሩትን መመለስ ፣ ትግሬዎችን በሁሉም መንግስታዊ ድርጅቶች የበላይነታቸውን ማረጋገጥና፣ በአይን አውጣነት በስፋት ትግሬዎችን እንዲቀጥሩ ማድረግ ፣ የተያዘው ስልት ይሄ መሆኑን አጫወተኝ ። ከተባረሩት መሃል ለመመለስ በሚደረገው ጥረትም፣ ለምሳሌ የትግራይ ፕሬዚደንት የአቶ አባይ ወልዱ ታላቅ ወንድም የሆኑት አምባሳደር አውአሎም ወልዱ፣ በአቶ መለስ ዘመን የተባረሩ ቢሆንም፣ በቅርቡ የመንግስት ቪላ እንዲሰጣቸው ተደርጓል ። የሚያሳዝነው በቪላው ውስጥ ላለፉት 20 አመታት ነዋሪ የነበሩት አንድ የቀድሞ ረዳት ሚኒስትር በ3 ቀናት ውስጥ ቤቱን ለቀው እንዲወጡ ተደርጓል አለኝ ።

ይሄ ሁሉ ሲሆን ብአዴኖች ምን እያደረጋችሁ ነው ስለው፣ እኛማ የአማራ ክልልን መሬት ለመንጠቅ የሚጋፉንን የትግራይ ክልል ወራሪዎች ስንከራከርና የህዝቡን ቁጣ ለማብረድ ላይ ታች ስንል፣ እነርሱ ፌዴራል መንግስቱን ትግራዋይ የማድረግ ስራቸውን እያፋጠኑ ነወደ አለኝ ። ከወልቃይት ሌላ ምን መሬት ፈለጉ? ብዬ ስጠይቅ፣ “ወልቃይት ትላለህ ጠገዴን አልፈው ሳንጃ እኮ ደርሰዋል ። ችግሩ በጣም ስለተባባሰ፣ ሃይለማርያም ደሳለኝ ራሱ መጥቶ ካድሬዎችን ሰብስቦ እስከማናገር ደርሷል ።

The post ያሬድ ጥበቡ ይናገራሉ: የኢትዮጵያ አየር መንገድ 85% የሚቀጥረው ትግሬዎችን ነው * አዲሱ ለገሰ ይህን ተቃውመው የቦርድ ሊቀመንበርነቱን ለቀዋል… ሌሎችም appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live