Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የሆሳህና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤ/ክ በእሳት ነደደች (ቪድዮና ፎቶዎች ይዘናል)

$
0
0


ቤተክርስቲያኗ ከመቃጠሏ በፊት

ቤተክርስቲያኗ ከመቃጠሏ በፊት

ከተቃጠለች በኋላ

ከተቃጠለች በኋላ

ከተቃጠለች በኋላ

ከተቃጠለች በኋላ


(ዘ-ሐበሻ) እኔ የዘ-ሐበሻ ሪፖርተር ነኝ ያሉ በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎች በፎቶግራፍ እና በቭዲዮ አስደግፈው በላኩት መረጃ የካቲት 21/2007 ዓ.ም በሀዲያና ስልጤ ሀ/ስብከት የሆሳዕና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤ/ክ በእሳት መንደዷን አስታወቁ፡

የቃጠሎው መነሻ እስካሁን ያልታወቀ ሲሆን ጉዳዩን ለማድበስበስ የሚደረገው ጥረት ም ዕመናኑን እያስቆጣ መሆኑንም ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ያመለክታል::

የካቲት 21 ቀን ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ ህዝበ ክርስቲያኑን ለማጽናናት እንዲሁም የገቢ ማሰባሰብ መርሐግብር የሀ/ስብከቱ ሊቀጻጻስ ብጹዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በተገኙበት ከአ.አ በመጡ መምህራን እና ዘማሪያን መርሐ ግብር ተዘርግቶ የነበረ ሲሆን ማንኛውም ም እመን የሚቻለውን ስፍራው ድረስ በመገኘት ድጋፍ እንዲደርግ ያልቻለም በጸሎት እንዲያስቡ በእግዚአብሔር ስም ቅድስት ቤተክርስቲያን ጥሪዋን አስተላልፋለች ሲሉ እኔ የዘ-ሐበሻ ሪፖርተር ነኝ ያሉ ከስፍራው ዘግበዋል::

ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው በዚሁ ቤተክርስቲያኒቱ በምትገኝበት ከተማ ከሳምንት በፊት በተመሳሳይ እሳት አደጋ አጠና ተራ ወድሟል::

The post የሆሳህና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤ/ክ በእሳት ነደደች (ቪድዮና ፎቶዎች ይዘናል) appeared first on Zehabesha Amharic.


አድዋ! –ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

$
0
0

hqdefaultዋ! አድዋ ፤ ያ ሑዳዴ

መድፍን ፈንጅን ፤ በጎራዴ

ባሕር ተሻግሮ ፤ የሐበሻን ምድር

ቅኝ ሊገዛ ፤ ይሄ ደፋር!

አንች አድዋ ፤ የበኩር ልጅ

ላንቺ ውልደት ፤ ስንቱ ሲፈጅ

ተጸንሰሽ ፤ ከውጫሌ

ለደም መሬት ፤ ለአሞሌ

እርግዝናሽ ፤ ዘጠኝ ወሩ

ዓመታትን ፤ ማስቆጠሩ

ክፉውን ቀን ፤ ይዞ አሳሩ

ከብቱ እረግፎ ፤ ባገር ምድሩ

ሰው ሁሉ አልቆ ፤ በችጋሩ

በፋሽስት ሸር ፤ በእኩይ ግብሩ

ከብት የሚፈጅ ፤ ደዌ ረጭቶ

በምን ታርሶ ፣ በምን ለምቶ

የገበሬው ፤ ሀብት ጠፍቶ

አከርካሪው ፤ ተመትቶ

የሚቀመስ ፤ እህል ታጥቶ

ረሀቡ ፤ ሕዝቡን በልቶ

ምኑ ተብሎ ፤ ስንቱን ነግሮ

የግፍ ግፉ ፤ ተዘርዝሮ

ዝም ይሻላል ፤ ምን ተቆጥሮ

በክፉው ቀን ፤ ራብ ደክሞ

ያለቀ ሕዝብ ፤ በአዋጅ ተሞ

በዚያ ድቀት ፤ ተጎድቶ

አፈር ልሶ ፤ ግድ ተነሥቶ

አይቀር ነገር ፤ የሀገር ጥሪ

ነፍሱ የሷ ፤ እሱ አኗሪ

ጉልበት ሆኖት ፤ የሀገር ፍቅሩ

አስቆጥቶት ፤ መደፈሩ

ገሰገሰ ፤ ወደ አድዋ

ጠላት ሊግት ፤ የሞት ጽዋ

አድዋ ላይ ፤ ከግንባሩ

ሊሞሻለቅ ፤ ሲተም ጦሩ

እንደ ሙላት ፤ ደራሹ ጎርፍ

ሲያስገመግም ፤ ጠላት ሊቀስፍ

ከተፍ ሲል ፤ ፊት ለፊቱ

ጥሊያን ራደ ፤ ልብ አጥቶ

ባለ የሌለ ፤ መሣሪያ አጉል

እያስጓራ ፤ ሲከላከል

በመድፍ አረር ፤ በመትረየስ

ግማሽ ሲቀር ፤ ሲሠዋ ነፍስ

ጠጋ ሲባል ፤ ወደ ምሽግ

ሌላ አሳር ፤ ምን ይደረግ?

በስል ችንካር ፤ በውጋቱ

በጠርሙስ ጦር ፤ በስለቱ

ምሽግ ማዶ ፤ በተከለው

አርበኛውን ፤ እንዲያስቀረው

ጠርሙስ አልፎ ፤ የፈንጅ ንጣፍ

ፋኖ የሚፈጅ ፤ በነፍስ ወከፍ

ያ ባዶ እግር ፤ ቢቀረደድ

ቢሸረከት ፤ ቢጎራረድ

ማን ተሰምቶት ፤ ለማን ታውቆ?

በፈንጅውም  ፤ ረግፎ አልቆ

ሊነሣ ይሻል ፤ ሞቶም ወድቆ

በወደቀው ፤ ተረማምዶ

ምሽግ ሰብሮ ፤ ጥሶ ንዶ

በጠላት ላይ ፤ ማት አውርዶ

ቆርጦ ሲጥል ፤ አንገት ጎርዶ

በፉከራ ፤ ቀልቶ አጭዶ

ሲፈጅ ሲማርክ ፤ ቆልቶ አሳዶ

ብቻ በሀገር ፤ በሕዝብ ፍቅር

በሚፋጀው ፤ እንደ ገሞር፡፡

አንች የረፋድ ፤ የድል ፀሐይ

የወጣሽው ፤ አድዋ ላይ

ከአባትሽ ፤ ከምኒልክ

ድባቅ መትቶ ፤ ካገባው ልክ

ከጣይቱ ፤ ከእናት ኩሩ

ፋኖዎቹ ፤ እያጋፈሩ

አድዋ ላይ ፤ ከአፈሩ

በቅዱሱ ፤ ጊዮርጊስ ለት

ተራድቶሽ ፤ ተርፈሽ ከሞት

ሰዓቱ ሲደርስ ፤ መወለጃሽ

በጭንቅ ምጥ ፤ የተወለድሽ

በሰው አጥንት ፤ በሰው ልጅ ደም

የታረስሽው ፤ የዓለም ሰላም

የሐበሻ ዘውድ ፤ የድል ማማ

በአጥንት ዕዳ ፤ በደም ጉማ

ምታስከፍይ ፤ ቃል ሲሰማ

ያችን ገልቱ ፤ ከንቱ ሮማ፡፡

አድዋ ቅኔ ፤ አድዋ ዜማ

የምትማርክ ፤ ምትስማማ

ለሰው ልጅ ልብ ፤ ያላት ግርማ

የአውሬን ልብ ፤ ምታደማ

በአፍታ ፍልሚያ ፤ ፈጣን ሽኝት

ወዲያው ብልት ፤ እዚያው ጥጥት

በአርበኛ ወግ ፤ በፋኖ ደንብ

ሳይገመት ፤ ሳይታሰብ፡፡

ነጭ በጥቁር ፤ በግፍ ገኖ

በጨካኝ ክንድ ፤ ይዞ አፍኖ

ጥቁሩ ሲኖር ፤ ተኮንኖ

መገልገያ ፤ ዕቃ ሆኖ

አሜን ወዴት ፤ አለሁ ብሎ

አንገት ሰብሮ ፤ ተገልሎ

በምድሪቱ ፤ በመላ ዓለም

በግፍ ሲኖር ፤ አጥቶ ሰላም

ለነጭ ተድላ ፤ ጥሮ ማስኖ

እሱ እንደሚያንስ ፤ ከልቡ አምኖ

ቅስም ሐሞቱ ፤ ነኩቶ ፈሶ

መራር ሐዘን ፤ ልቡ ውስጥ ነግሦ

ሲኖር ዘወትር ፤ ቀንበር አዝሎ

አድዋ ላይ ፤ የድሉ አውሎ

አሽቀንጥሮ ፤ ሸክሙን ጥሎ

ነጩን እባብ ፤ ላይድን ገሎ

አነሣለት ፤ ከስር ነቅሎ

አስበርግጎ ፤ አስደንብሮ

ፈነቃቅሎ ፤ ጥልቅ ሰርስሮ፡፡

እናም ዓለም ፤ ተገደደ

ውዳቂ ሐሳብ ፤ በግድ ካደ

አዲስ ታሪክ ፤ ተሰነደ

የተጠላው ፤ ተወደደ

ሰው መሆኑን ፤ የአዳም ዘር

ከነጭ ቢጫ ፤ ከቀይ ፍጡር

እንደማያንስ ፤ ምን ቢጠቁር

አረጋግጦ ፤ ቆመ በክብር

እድሜ ለዚያች ፤ የድል ፀሐይ

ለበራችው ፤ አድዋ ላይ

የባርነት ፤ ሰንሰለቱን

በጣጠሰ ፤ እግር ብረቱን

ተቀዳጀ ፤ ነጻነቱን

ቀበረለት ፤ ባርነቱን

የሀገሩ ፤ የመብቱ

ራሱ ሆነ ፤ ባለቤቱ

ዕድሜ ለዚያች ፤ የድል ፀሐይ

ለበራችው ፤ አድዋ ላይ

የምዕት ዓመታት ፤ ጣር ጨለማ

ተወገደ ፤ ድል ተሰማ

ያች ፀሐይ ፤ የድል ጮራ

ደማቅ ጸዳል ፤ የገድል አውራ

የከበረች ፤ ስጦታ ናት

ምንም ነገር ፤ የማይተካት

ከሐበሻ ሕዝብ ፤ ለጥቁር ዘር

ለተገፋው ፤ ለበላ አሳር፡፡

የካቲት 19 2007ዓ.ም.

The post አድዋ! – ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው appeared first on Zehabesha Amharic.

በቤይሩት ኢትዮያዊቷ ራሷን አጠፋች በሚል ሰበብ….. ኤምባሲው ያለምንም ምርመራ ሬሳዋን አሳፍሩ ማለቱ ብዙዎችን አሳዘነ

$
0
0

በግሩም ተ/ሀይማኖት
ኢትዮጵያዊኖች በአረብ ሀገራት ስደታቸው ጥሩም መጥፎም ይገጥማቸዋል፡፡ ብዙ ጊዜ ራሳቸውን አጠፉ በሚል ሰበብም አሰሪዎቻቸው ይገሏቸዋል፡፡ እንዴት ሞቱ የሚል ማጣሪያ ወይም ምርመራ አይደረግም፡፡ ከተቻለ ሬሳቸው ይላካል ካልሆነም ፍሪጅ ውስጥ ተቀምጦ ለተማሪዎች መለማመጃ ይደረጋል፡፡ የሚፈለግ አካልም ይወሰዳል፡፡ ሁሌም ይሄው ነው፡፡
ethiopian woman Arabባለፈው ሳምንት ሰኞ ዕለት ቤይሩት ውስጥ ሳይዳ ሀበፊ የተባለ አካባቢ አንዲት ኢትዮጵያዊት ሞተች፡፡ በአሰሪዎቿ በኩል ራሷን አጠፋች ነው የተባለው፡፡ በፎቶው ላይ እንደምታዩት ከልጅቷ ቁመት ያነሰ መስኮት ላይ ገመድ አስራ ነው ታንቃ የሞተችው ያሉት አሰሪዎቿ፡፡ ራሷን ለማጥፋት የሚያበቃ ምንም አይነት ችግር አልነበረባትም፡፡ ለሞት የዳረጋትን ነገር ቢያስቡ ቢያሰሉ የሚያገኙት ፍንጭ በማጣታቸው በርካታ ጓደኞቿ በሁኔታው ከፍተኛ የሆነ ጥርጣሬ አደረባቸው፡፡
እንዴት ከእሷ ቁመት ባጠረ ቦታ ላይ ታንቃ ሞተች? ሁኔታው አጠራጣሪ ነው ብለው ቤይሩት ላለው ኢትዮጵያ ኤምባሲ ደጋግመው ጥርጣሬያቸውን አመለከቱ፡፡ ኤምባሲው ከወትሮ አሰራሩ የተለየ ሁኔታ የለውም፡፡ በእነአለም ደቻሳ ጊዜ የታየው አለመቆርቆር መልኩንም ቅርፁንም አለወጠም፡፡ እንዲያውም ችላ ባይነቱን አሳድገውት የወሰዱት ርምጃ ብዙዎችን ያሳዘነ፣ እንባ ያራጨም ሆነ፡፡
መቼ ይሆን ለሞታችን መብታችን ለመረገጡ ሰሚ እና ተከራካሪ የምናገኘው የሚለው የዘውትር ጥያቄ ደጋግሞ ብልጭ እንዲል አደረገ፡፡ ኤምባሲው ለሉብናናዊቷ አሰሪ ስልክ በመደወል ያላትን እቃ ሰባስባችሁ አምጡ፡፡ በቃ!….
ለልጅቷ ቤተሰቦች ደውለን እንዲከሱ ለማድረግ ቢሞከርም ስልካቸው ሊነሳ አልቻለም፡፡ ያለው አማራጭ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማሳወቅ ነውና ይህን ተግባር አከናወንን፡፡ መፍትሄ ይገኝ ይሆን? ሬሳዋ ፍሪጅ ውስጥ ተቀመጦ ቀረ፡፡ መቼ አስታውሰው ይልኩት ወይም ይቀብሩት ይሆን? ኢንሹራንሷንስ ኤምባሲው ዝም ይል ይሆን? ያነጋግራል፡፡

The post በቤይሩት ኢትዮያዊቷ ራሷን አጠፋች በሚል ሰበብ….. ኤምባሲው ያለምንም ምርመራ ሬሳዋን አሳፍሩ ማለቱ ብዙዎችን አሳዘነ appeared first on Zehabesha Amharic.

“ዜና አትስሙ”ለሚለው ፓስተር ምላሽ –ክንፉ አሰፋ

$
0
0

በከፊል የተቀዳውን የፓስተሩን ንግግር የሰማሁት “ሰልማ”  የተሰኘውን ፊልም አይቼ እንደተመለስኩ ነበር። በዚህ አመት ለአራት የኦስካር ሽልማት የበቃው “ሰልማ” ፊልም ኦፕራ ዊንፍሬን ጨምሮ ምርጥ አክተሮች ይተውኑታል። ፊልሙ እ.ኤ.አ. በ1965 በዩናይትድ ስቴትስ የጥቁሮች የመምረጥ መብት ገፈፋን ተከትሎ፣  ዶክተር ማርቲን ሉተር ይህ መብት እንዲከበር የሚያደርገውን ትንቅንቅ ያሳየናል።  ፓስተር  ሉተር ለዜጎች የመምረጥ መብት እንዲከበር ያለማቋረት በመስበኩ ሲደበደብ፣ ሲንገላታና ሲታሰር እናያለን። በአላባማ ግዛት የሚኖሩ ጥቁሮች መብታቸውን ስለጠየቁ ብቻ የመርዝ ጭስ ቢረጭባቸው፣ ቢደበደቡ፣ ቢታሰሩ እና ቢገደሉም ሉተር ተስፋ አልቆረጠም።  ሰቆቃውን በብሄራዊ ቴሌቭዥን የሚያዩ ሁሉ በቁጭት ትግሉን ተቀላቀሉ።  ከግዜ  በኋላም የ”ሰልማ” እና የ”ሞንትጎመሪ” ጥቁሮች የመምረጥ መብታቸው ተጠበቀ።  በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተውን ይህንን ፊልም የሚያዩት ሁሉ በእንባ ይታጠቡ ነበር።

እዚህ ላይ ተስፋ ያለመቁረጥን ብቻ ሳይሆን የሜድያን ሚና፣ በተለይ ደግሞ የቴሌቪዥንን ሃይል እናይለን። ዘረኞች እና አንባገነኖች ሜዲያን የሚጠሉት ያለምክንያት አይደለም። በዩናይትድ ስቴትስ ዘረኝነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ የመገናኛ ብዙሃኑ ነጻ በመሆኑ ህዝቡን ነጻ ሊያወጣው ችሏል።

የኛ ፓስተር ደግሞ ጭራሽ “ዜና አትስሙ” ሲል ይደመጣል። በዚያ በተነሳሽነት እና በቁጭት ስሜት ሆኖ የፓስተሩን ንግግር ለሚሰማው ደግሞ በጣም ያበሳጫል።  “አትስሙ” ሲል የመስማት መብትን መጋፋቱን አላስተዋለው ይሆናል። ፓስተሩ በዚህ አላበቃም የኢሳት ሰዎች ቅዥታሞች ናቸው ሲልም ይዘልፋል። ቀን ከለሊት ይቃዣሉ ሲል ፍርድ ሰጥቷል። ፍርድ ለመስጠት እርሱ ማን ሆኖ? መጽሃፍ የሚለን “አትፍረድ ይፈረድብሃል” ነው።

ክፉውን ነገር አትቃወሙ የሚል ነገር በመጽሃፍ ቅዱስ የለም። እንዲያውም በብሉይ ዘመን ነብያት የገዥዎችን ክፉ ስራ ያወግዙ ነበር። ይህ ሰው መንፈሳዊ ነኝ የሚለን ከሆነ ኢትዮጵያ በሚሰራውን ክፉ ነገር አንዲት ቀን ተቃውሞ ያውቃል?

ቄስ ወይንም ፓስተር ሲሆኑ ስራቸው ወንጌልን መስበክ ነበረበት። “ዜና አትስሙ” ማለት ወንጌል አይደለም። ፖለቲካ ነው። ለዚያውም ያንድ ወገን ፖለቲካ። እንዲህ አይነት መልእክት በቤተ-ክህነት ውስጥ ማስተላለፍ መንፈሳዊነት አይደለም። ንግግሩ  የጉባኤውን የግንዛቤ አቅም ዝቅ ከማድረግ የሚመጣ ንቀትም ይመስላል።

በኢትዮጵያ ያለው እውነታ ይህ ነው። ዜጎች በሽብር ስም ይታሰራሉ፣ ሰዎች ያለአግባብ ይሰቃያሉ፣ ወገኖቻችን ያለአግባብ ይገደላሉ፣…  መሬታቸው ለባእዳን እየተሰጠ ይፈናቀላሉ፣ ባለስልጣናቱ ያለ አግባብ ሃብት እያካበቱ ነው፣ ምርጫ ይጭበረበራል…. ዜናዎቹ እነኝህ ናቸው። ይህንን ሰምቶ የራሱን ግንዛቤ የመስጠት መብቱ የሰሚው ነው። ይህንን አትስሙ ማለት ምን ማለት ነው?
ESat

ዶክተር ማርቲን ሉተርም ፓስተር ነበር። ህልም ያለመ ፓስተር። ዜና ከመስማት ባሻገር ህዝብን ለመብቱ እንዲነሳ የሰበከ ፓስተር። በአመጽ-አልባ ትግል የጥቁሮችን መብት ያስጠበቀ ፓስተር። ፐሉተር ህልም የጥቁሮች የመምረጥ መብት  ብቻ ላይ አላበቃም።  አንድ ቀን ጥቁር ሰው ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካን  ይመራታል ብሎ ነበር። ይህ ህልሙ ከሞላ ጎደል በባራክ አኦባማ እውን ሆኗል።

እንዲህ አይነት አመለካከት ላላቸው የሃይማኖት መሪዎች፤ ዲታቆን፣ ቄስም ሆነ ፓስተሮች በሙሉ አንዲት መል እክት አለችኝ። ህልም ባይኖራችሁም፣ የዜጎች ህመም ባይሰማችሁም፣ ግፍን መቃወም ባትፈልጉም፤  ዝም ብላችሁ ወንጌልን ብቻ ስበኩ።  መንፈሳዊ ባልሆነ ንግግር የሌላው መብት አትጋፉት።

The post “ዜና አትስሙ” ለሚለው ፓስተር ምላሽ – ክንፉ አሰፋ appeared first on Zehabesha Amharic.

የአድዋ ድልና እኛ –ዳንኤል አበራ

$
0
0

ይህ የአድዋ 119ኛ አመት መታሰቢያ እኛና አድዋ በተሰኘ ርእሰ ጉዳይ ላይ ያተኩራል። ድርሰቱ ስድስት ንኡሳን ክፍሎች አሉት። ሁላችንም በጦርነቱ በድሉም ወቅት ስላልነበርን የተጻፈ አንብበን ከምናውቀው አመሳክረን ነው ጽሁፉ የተዘጋጀው። የተጻፈ አንብበን ላልኩት የጳውሎስ ኞኞን ምክር ከልቤ አድርጌ ነው። ጳውሎስ ኞኞ ኢጣሊያና የኢትዮጵያ ጦርነት በሚለው መጽሃፉ እኛ ስለራሳችን ስንጽፍ እናጋንናለን ስለዚህ የውጭ አገር ምእራባውያን የመሰከሩልንን ተጠቅሜያለሁ ይላል። የጳውሎስ አንደኛውን ምክር ከልብ ማድረግ ነው። ሁለተኛ ቢያሳዝንም እውነት ስለሆነ የሰዎች ስም በክፉ ይነሳል፤ አያት ቅድመ አያት ለሰራው ባንጠየቅም የአያቶቻችን ስም ሲነሳ አለመቀየም ነው። ከተቀየማችሁም ምን ይደረጋል ከመጻፍ አይቀርም። ራስ ደስታ ዳምጠው በሁለተኛው የጣሊያን ጦርነት የደቡቡን ውጊያ የመሩ ለጣሊያን ባደረ ሀበሻ ጠቋሚነት ነው ተይዘው የተገደሉት። አባታቸው ፊታውራሪ ዳምጠው ከተማ በትግራዩ ጦርነት ነው የተገደሉት። አባትም ልጅም ተሰውተዋል ሲሆን እንዲህ ነው። ባንዳ በክፉ ይነሳል የባንዳ ልጅ ባንዳ ከሆነ ምን ይደረጋል? ባይሆን ልብ መግዛት ነው።

=—-[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

Adwavictory

Download (PDF, 482KB)

The post የአድዋ ድልና እኛ – ዳንኤል አበራ appeared first on Zehabesha Amharic.

የእሳት አደጋ በሆሳዕና ማርያም –ስለ ቃጠሎውና ከኛ ምን እንደሚጠበቅ (ከዘመድኩን በቀለ)

$
0
0

ከዘመድኩን በቀለ

በቅርቡ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል በኩል ጣና ሐይቅ ላይ በሚገኘው ጥንታዊው የዳጋ ቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም ውስጥ ተነስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በእግዚአብሔር ቸርነት በመጥፋቱ ሁላችን እጅግ ደስስ ብሎን የነበረ ቢሆንም እሳቱ እጁን አርዝሞ አሁን ደግሞ ወደ ደቡብ ክልል ወርዷል ።

በትናንትናው እለት ደግሞ ከወደ ደቡብ በሃድያና ስልጤ ሃገረ ስብከት ከሆሳዕና ከተማ የተሰማው ዜና እጅግ የሚያሳዝንም የሚያስቆጭም ነው። ለጊዜው የእሳቱ መንስኤ ባይታወቅም ከተመሰረተች 106 ዓመት የሆናት የታሪካዊቷ የሆሳዕና ደብረ ገነት የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት መውደሙን ከስፍራው የደረሰኝ በቪድዮ የተደገፈ መረጃ ያሳያል።

ጉዳዩን የበለጠ ለማጥራት እኔም የሀገረ ስብከቱን ዋና ስራ አስኪያጅ ክቡር ቆሞስ አባ ቢንያም ማንቾ እና የደብሯን አስተዳዳሪ መልአከ ምህረት ቀሲስ አስናቀን በስልክ አግኝቼ አነጋግሬያለሁ ። ሁለቱም አባቶች የእሳት አደጋው መንስኤ አሁን ላይ እንዲህ ነው ብለን መናገር ባንችልም የጥንቃቄ ጉድለት መሆኑ ግን ሚዛን እየደፋ በመሄዱ ግን ይስማማሉ ።

በተለይ የደብሯ አስተዳዳሪ እንደነገሩኝ ከሆነ ፤ ዕለቱ ቀዳሚት ሰንበት ፣ በዓሉም የእመቤታችን ወርሃዊ በዓል በመሆኑ ሥርዓተ ቅዳሴው በጠዋቱ 2 ሰዓት ላይ ተፈጽሞ እኛም ቤተክርስቲያኑን ዘግተን ቢሮ እንደተቀመጥን ፣ ምእመናንም ቤተክርቲያኗን ከብበው ጠበል ጻዲቁን እየቀመሱ ሳለ ነው ከቤተመቅደሱ ውስጥ እሳቱ ተነስቶ ሁሉም ተጯጩሆ ለማጥፋት ርብርብ የተደረገው ብለው አጫውተውኛል ።

የእሳቱን መነሳት ዐይተን የድረሱልን ጥሪ ደወል በመምታት እንዳሰማን ፣ ጭሱን እና ጥሪውን የሰሙ ሁሉ ዘር እና ሃይማኖት ሳይለዩ በሙሉ መጥተው በእሳት ማጥፋት እንቅስቃሴ ላይ ተሳትፏል ።
እሳቱ ከባድ ጉዳት በቤተክርስቲያኗ ላይ አያድርስ እንጂ በቤተመቅደሱ ውስጥ ጽላቱ ምንም እንዳልሆኑ የደብሩ አስተዳዳሪ አክለው ነግረውኛል ። እግዚአብሔር ይመስገን ።

በቤተክርስቲያኗ ቅፅር ግቢ ውስጥ በተደረገው ጊዜያዊ የገንዘብ ማሰባሰብ ሥራ ላይም የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያንና የእስልምና እምነት ተከታዮችና መሪዎች እንዲሁም የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ደገለ ኤርጌኖ ፣ የዞኑ የፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አበራ አይደሞና የከተማዋ ከተማ ከንቲባም በግንባር በመቅረብ በግላቸው አስተዋፅኦ ከማድረጋቸውም በተጨማሪ እስከመጨረሻው በቤተክርስቲያኗ ሥራ ላይ በግላቸው ጭምር ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል ብለውኛል እኒህ ሁለቱ የቤተክርስቲያን አባቶች አባ ቢንያም እና ቀሲስ አስናቀ ።

ቤተክርስቲያኗ ከመቃጠሏ በፊት

ቤተክርስቲያኗ ከመቃጠሏ በፊት

በሁኔታው ማዘን እና ማለቀሱ ብቻውን ዋጋ የለውም ። ይልቁንም ለተሻለ ሥራ እንድንነሳ ያስፈልጋል ።እናም በዚህ አጋጣሚ እኔ አንድ ኃሳብ በኢትዮጵያና በመላው ዓለም ለሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን በትህትና አቀርባለሁ ።

።።።። ባለሙያዎች ።።።።

፩ኛ ፣ የቤተክርስቲያን ልጆች የሆናችሁና የአርክቴክቸር ሙያ ያላችሁ የቤተክርስቲያን ልጆች ግሩምና ድንቅ ታሪካዊ የሆነ ዘመን ተሻጋሪ የቤተክርስቲያን ዲዛይን በነፃ ብታዘጋጁ ።

።።።። ምእመናን ።።።።

፪ኛ፣ ይህን ዜና የሰማን እኛ በመላው ዓለም ያለን የቤተክርስቲያን ልጆች ሀብታም ድሃ ሳንል ሁላችን በአንድነትና በአጭር ጊዜ ውስጥ እግዚአብሔር ከሰጠን ውስጥ ያለንን ገንዘብ ብናዋጣ ፣
።።።። የደብሩ አስተዳደር ።።።።

፫ኛ፣ የደብሩ አስተዳደር ቤተክርስቲኗን መልሶ ለመገንባት ይቻል ዘንድ አንድ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ቢያዘጋጅ ። በአስቸኳይም የህንፃ አሰሪ ኮሚቴ አቋቁሞ የባንክ ሒሳብ ቁጥር ይፋ ቢያደርግ ።
።።።። ማኅበራት ።።።።

በባለሙያዎች የተደራጀው የቤተክርስቲያናችን መመኪያ የሆነው ማኅበረ ቅዱሳን ፈጣን የሆነ ምላሹን እንጠብቃለን ። የጉዞ ማኅበራት ያላችሁ ወንድሞች ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት መንገዶችን ሁሉ ወደ ሆሳዕና ማድረግ ይጠበቅባችኋል የሚል ሓሳቤን አቀርባለሁ ።
በእኔ በኩል የሚጠበቅብኝን ሁሉ ለማድረግ ፈቃደኛም ዝግጁም መሆኔን እገልፃለሁ ። ለጉባኤው መሳካት ይረዳ ዘንድ ወዳጆቼን ፣ እኔን ራሴን ጨምሮ ጓደኞቼን በማካተት ስፖንሰር በማፈላለግ ለቅድስት ቤተክርስቲያን እንድረስላት ።
ሆሳዕናዎች አይዟችሁ አለን ከጎናችሁ ። አበው ” ሃምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ ለሃምሳ ሰው ግን ጌጡ ነው እንዲሉ ፣ እኛም እንረባረብ ።
አሁን በደረሰኝ ዜና መሰረት ኮሚቴ እስኪቋቋም ድረስ ደብሩ በጊዜያዊነት ዝግ የባንክ አካውንት በሆሳዕና ከተማ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባቴና ቅርንጫፍ የባንክ ሂሳብ ተከፍቷል ። ቁጥሩም 1000110719969 እንደሆነ ይፋ ሆኗል ።

እኔ ይህን ብያለሁ እናንተም የምትሉትን በሉ በዚህ ጽሑፍ ላይ Comment አና Share ይበረታታሉ ።
ዘመድኩን በቀለ ነኝ
የካቲት 22 /6/2007 ዓም
አዲስአበባ — ኢትዮጵያ

The post የእሳት አደጋ በሆሳዕና ማርያም – ስለ ቃጠሎውና ከኛ ምን እንደሚጠበቅ (ከዘመድኩን በቀለ) appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢሳያስ አፈወርቂን በጨረፍታ (ክንፉ አሰፋ)

$
0
0
isayas afewerki

ኢሳያስ አፈወርቂ

 

“አንድም ቀን ስቀን አናውቅም!” አሉ ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማርያም። ይህን በሚሉ ጊዜ እፊታቸው ላይ ፈገግታ ይታይ ነበር – ምሬቱ እንዳለ ሆኖ። ኢሳያስ አፈወርቂ ሲስቁ አይተናቸው አናውቅም። ግን ኮስተር ብለው የሚናገሩት ነገር እኛኑ አያሳቀን ነው። “ካሳ ይገባናል! ካሳ ስጡን” ሲሉ አሳቁን። ቀጠል አድርገውም “ምጽዋና አሰብን ወያኔ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲጠቀምበት ፈልገው” እንደነበር ተናግረው አሳቁን። “…የሰራነው ጥፋት ስለሌለ የሚጸጥተን ነገር የለም።” አሉ እጃቸውን እንደ ጲላጦስ እያጠቡ። ከዚህ ቀደም ለስዊድኑ ጋዜጠኛ የአስመራው የፖለቲካ ስርዓት ስዊድን ካለው ስርዓት የተሻለ እንደሆነ አስረግጠው ነገሩት። ስለ ብሄራዊ ምርጫ ለጠየቀቻቸው የአልጃዚራዋ ጋዜጠኛም “ምርጫ ምንድነው?” ብለዋት ነበር። ከዚህ በላይ ምን የሚያስቅ ነገር አለ?

የፈለጉት ካሳ ግን ምን ይሆን? የገንዘብ ካሳ፣ የሞራል ወይንስ የሃገር? ….  ጾረና፣ ዛላምበሳ፣ ባድመ? ወይንስ ኢትዮጵያ!?

“በዋልድባም ባመት አንዴ ይዘፈናል።” ይባላል። ኢሳያስ አፈወርቂስ ባመት አንዴ ብቅ እያሉ ስለ ኢትዮጵያ የፈለጉትን ቢናገሩ ምን ይላቸዋል? በዚያ ላይ አሁን “የኢትዮጵያ ወዳጅ” ሆነዋል።

ናሳ የተባለው የአሜሪካ የጠፈር ምርምር ተቋም የአፍሪካ ቀንድን በሳተላይት ፎቶ አንስቶ ነበር። በፎቶው ላይ ሲታይ ኤርትራ ሙሉ በሙሉ አረንጓዴ ነበረች። ሳይንቲስቶቹ ይህችን ቆላማ ሃገር እንደሚወራው በረሃ ሳይሆን ይልቁንም ከጠበቁት በላይ ለም ሆና ተመለከቷት። ከሺዎች ኪሎሜትር የተነሳውን ይህንን ምስል እያቀረቡ ሲመለከቱት ግን ነገሩ ሌላ ሆኖ አገኙት። ከሩቅ የለመለመ ቅጠል መስሎ የሚታየው ነገር አረንጓዴው የወታደር ልብስ ኖሯል። ሳዋ፤ ትልቁ የኢሳያስ አፈወርቂ ዩኒቨርሲቲ ከህጻን እስከ አዛውንት እያስገባ ውትድርና ያሰለጥናል። በኤርትራ ዛሬ ሁሉም ዜጋ ወታደር እንዲሆን ተገዷል። የወያኔን ስርዓት በሃይል ለመጣል በአስመራ ጦር ያሰፈሩ የተቃዋሚ ሃይሎች ቁጥርም ቀላል አይደለም። አረንጓዴ የለበሱ እነዚህ ሃይሎች እድሜያቸውም ሁለቱን አስር ሊነካው ነው።

የኢሳት ጋዜጠኞች ኢሳያስን ለጠየቋቸው አንደኛው ጥያቄ ምላሹ ይኸው ነው። ሁሉም አረንጓዴ ለባሽ፣ ሁሉም ነጭ ለባሽ በሆነበት ሃገር ማን ማንን ሊጠብቅ ይችላል?  ”ባለስልጣናቱ ሁሉ ያለ አጃቢ የሚሄዱበት ምክንያት ምስጢሩ ምንድነው?” የሚል ነበር ጥያቄው። ጥያቄዋ አቅጣጫ ቀያሽ ጥያቄ ስለነበረች ለኢሳያስ አፈወርቂ እንደተመቻቸው ያስታውቅባቸዋል። መልስ ሲሰጡ ንፅፅር ውስጥ ገቡና እድሉን ባላንጣዎቸውን ለመምቻ ተጠቀሙበት። ባላንጣቸው ህወሃት ብቻ አይደለም። ምእራቡም፣ ምስራቁ ዓለም የእሳቸው ጠላት ነው።

በሁሉም ጉዳይ ላይ ባዕዳንን ይወቅሳሉ። እዚህ ላይ እውነት አላቸው። ታሪክ እንደሚነግረን ለሃያላን ሃገሮች አልንበረከክ ያለች ኢትዮጵያን ለማዳከም የባህር በር ማሳጣቱ ሴራ በባእዳን ነው የተጠነሰሰው። እሳቸውም ምስጢሩን በደንብ አድርገው ያውቁታል። ይህን ሴራ እውን ለማድረግ በቱርክና በግብፅ ከዚያም በጣሊያንና በእንግሊዝ ብዙ ተሞክሮ ነበር። የጉንደት፣ የጉራ፣ የኩፊት፤ የኮቲት እና የዶጋሊ ጦርነቶች ለዚህ ዋቢ ናቸው። ሁሉም አልተሳኩም። ይህንን የቤት ስራ በመጀመርያ ጀብሃ ከዚያ ቀጥሎ ሻእቢያ ከባእዳን ተቀብሎ መስራት ጀመረ። የነዚህ ባእዳን ህልም በመጨረሻ በኢሳያስ አፈወርቂ እውን ሆነ። 5 ሚሊዮን ህዝብ ላይጠቀምበት የሁለት ወደብ ባለቤት ሲሆን፣ 80 ሚሊዮን ህዝብ ግን ያለ ወደብ እንዲኖር ተደረገ።

እኝህ ሰው የርስበርስ ጦርነቱን አሸንፈው ኤርትራን ባስገነጠሉ ጊዜ ጀግና ነበሩ። የግዜ እንጂ የሰው ጀግና የለምና የጀግንነታቸው ጫጉላ እንዳሰቡት ረጅም አልዘለቀም። “ነጻነቱን” በቅጡ ሳያጣጥሙት ሌሎች ጦርነቶች ውስጥ ገቡ። ትልቁ እና ዋነኛው ጦርንርት ግን ከሕዝባቸው ጋር የገጠሙት ፍልሚያ ነው። ውጤቱም ስደት ሆነ። ዛሬ የኤርትራን ምድር ለቅቆ ለመጥፋት የማይጥር ዜጋ የለም። በኮንቬንሽናል ጦርነት ጊዜ ከሚሰደደው ህዝብ የበለጠ ቁጥር ያለው ህዝብ ይሰደዳል። ከኤርትራ ህዝብ ብዛት አንጻር ሲታይም ስደተኛው እጅግ ብዙ ነው። የተሳካለት የኤርትራ ተወላጅ በረሃ አቋርጦ ኢትዮጵያ፤ ሱዳን እና ሊቢያ ይዘልቃል። ያልተሳካለት ደግሞ በየጠረፉ የሻእቢያ ራት ይሆናል። የዜጎች ኩላሊት ሽያጭም እዚያው ይካሄዳል። በኤርትራ እንደቀልድ የሚነገር እውነታ አለ። ኢሳያስ አፈወርቂ ለኤርትራ ካበረከቱት ነገር ሁሉ የኢቦላ ወረርሽኝ በሃገራቸው እንዳይገባ ማድረጋቸው ነው። ከዚያ የሚወጣ እንጂ የሚገባ ሰው ስለሌለ።

በዚህ ዘመን ከሚከሰቱት እልቂቶች ሁሉ የላቀ እልቂት እና ሰቆቃ የምናየው በነዚህ ወገኖቻችን ላይ ነው። ስንት ኤርትራውያን እንደበላች የሲሲሊዋ ላምባዶዛ ትመስክር።

“ጽድቁ ቀርቶ፣ በቅጡ በኮነነኝ” ይላሉ አበው። የካሳውን ተረት ለጊዜው እንተወውና፣ ታሪክ ኢሳያስን የሚዘክራቸው በተያያዙት የግፍ አስተዳደራቸው ይሆናል። በለስ ቀንቷቸው የኤርትራን ምድር ነጻ ቢያደርጓትም ህዝቡ ግን ነጻነትን እንደናፈቀ እነሆ 23 ዓመታት አለፉ። ህዝበ ኤርትራ ነጻ አልወጣም። ኢኮኖሚውም እንደ ቤተ-ጸሎት በአስራት ላይ ነው መሰረቱ። ነጻነትን ሳያያት፤ የነጻነትን አየር ሳይተነፍስ ሁለት አስርተ አመታት እንደዋዛ አለፉ። ለኢሳያስ፣ ሀገርን መምራት አመጽን እንደመምራት ቀላል አልሆነላቸውም። ሰላምን ማሸነፍ፣ ጦርነትን እንደማሸነፍ አልሆነላቸም።…

ኢሳያስ አፈወርቂ ዳግም ከኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ጋር ተቀምጠው አየን። የቀረበላቸውን ጥያቄዎች ሁሉ ሰማን። መልሶቹንም አደመጥን። አደመጥን ማለቱን የመረጥኩት ያለ ምክንያት አይደለም። በአሁን ዘመን ብዙዎች ይሰማሉ እንጂ አያዳምጡም። ለወቀሳውም፣ ለትችቱም ሆነ ለክርክሩ አመቺ ሚሆነው ከመስማት ይልቅ ማዳመጥ ሲቻል ነው። የማይደመጥ ነገር በአብዛኛው የተዛባ ትርጉም ተሰጥቶት ነው የሚቀርበው።

ታዲያ አዲሱን ቃለ-ምልልስ እንዳደረጉ በማስታውቂያ ከተነገረ በኋላ ለመስማት ትንሽ  አስጠበቁን። በመጀመርያ የትግርኛው ምላሽ ተተርጉሞ እስኪቀርብ ተጠበቀ።  ከግዜ በኋላ ደግሞ የእንግሊዝኛውን ጠብቁ ተባልን። አዲስ ነገር እንዳለ ለመስማት እንደ ሰስፔንስ ፊልም ልብ እያንጠለጠሉ አከረሙን። ያም ሆኖ “ከጸሃይ በታች ምንም አዲስ ነገር የለም” ብለን አልደመደምንም። ቢያንስ አዲስ ቀልድ ይዘውልናል…. ከጸደቁ አይቀር ግን በአማርኛ ተናግረው ቢጸድቁብን መልካም ነበር። ስራውም ይቀል ነበር። ሁላችንም የምንግባባበት አማርኛ ጠፍቷቸው ነው እንዳንል፤ ደሴ ወይዘሮ ስህን ትምህርት ቤት ነው የተማሩት። ከዚያም በቀዳማዊ ሃይለስላሴ ዩንቨርስቲ የነፃ ትምህርት ዕድል ተሰጥቷቸው ይማሩ ነበር። የፈረንጅኛው ቋንቋ ሊቀልላቸው ይችላል። የሚቀርባቸው ግን አማርኛ ነው።  ሃሜተኞች እንደሚሉት ኢሳያስ አፈወርቂ ለኢትዮጵያውያን የቤት ስራ መስጠት ስለሚወዱ ነው በአማርኛ ለመናገር ያልፈለጉት። ከዚህ በፊት የመቶ አመት፤ አሁን ደግሞ የመቶ ሰዓት የቤት ስራ።…

በአንድ ግዛት ውስጥ ሆነን ለሺዎች ዓመታት የኖርን፤ በቋንቋ፣ በታሪክ፣ በሃይማኖትና በሥነ ልቦናም አንድ የነበርን ህዝብ እንደሆንን ይሰማኝ ነበር። እንገንጠል አሉ። ገነጠሉዋት። ኤርትራ በጂኦግራፊም ሆነ በስትራቴጂ አቀማመጥዋ የኢትዮጵያ ራስ ነበረች ብለው የሚያምኑ ወገኖች በወቅቱ ሄዱብን ነበር ያሉት። ይህች ክፍለ-ሃገር ራስ ሳትሆን ራስ-ምታት ነበረች የሚሉት ወገኖች ደግሞ ሄዱልን ብለው ነበር።

ዛሬ ራስ ምታቱ ሲጸናባቸው እነሆ እየመጡ ነው። ዳግም ከኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ጋር ተቀምጠው አየን። ስለኢትዮጵያ ብቻ ይናገራሉ። ስለ ህዝቡ ይቆረቆራሉ። የኢትዮጵያ ችግር እንቅልፍ እንደነሳቸው ያወራሉ። ከዚህ ቀደምም ከኤልያስ እና ስለሺ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ። “… ያለፈውን እንርሳ። የታሪክ ባሮች አንሁን። ኑና እንወያይ።” ማለታቸውን እናስታውሳለን። መወያየት መልካም ነገር ነው። ለውይይት ግን ወቅትም ይወስነዋል። ያኔ በ99.9 በመቶ ውጤት ከተጠናቀቀው የሪፈረንደም ጫወታ በፊት “ኑና እንወያይ።” ቢሉን አሁን የገቡበት ችግር ውስጥ ላይገቡ ይችሉ ነበር።

በአንድ በኩል ከኢትዮጵያ የመለየቱ ቁጭት እንዳለ እናያለን። ደፍረው አልተናገሯትም እንጂ ስህተት እንደሰሩ ከሚሰጧቸው ቃለ-ምልልሶች መረዳት አያዳግትም። ለኢትዮጵያ ሕዝብ የመቆርቆሩ ጉዳይ ግን የአዞ እንባ ይመስላል። እዚያው እጉያቸው ላሉት ኢትዮጵያውያን ያልራሩ፣ መረብን ተሻግሮ ማሰቡ ግብዝነት ነው የሚሆነው።

በመጀመርያ አይናቸውን ጠረግ ጠረግ አድርገው የራሳቸውን ቤት ችግር ማየት ሲችሉ፣  የሌላውን ችግር አጥርተው ለመመልከት ይሳናቸዋል።

በቃለ-መጠይቁ ላይ ገጽታቸው እንደመሪ አይደለም። ሰውነታቸው ተጎሳቁሏል፣ ፈታቸውም ጠውልጓል። ከላይ ያጠለቁት ልብሳቸው የተጨማደደ ነበር። ከነበሩበት ደከም ያለ ጣራ ስር ሆነው፤ ግና ዘና ብለው በለሰለሰ አንደበት ይናገራሉ። የኢሳያስን ገጽታ የሚመለከቱ  ሰዎች በሌላ ሊተረጉሙት ይችላሉ። ራስ ወዳድ ያልሆኑ፤ ለግል ኢጎዋቸው የማይጨነቁ… ይባሉ ይሆናል። እንዲህ አይነቱ  ሁኔታቸውን ዋቢ በማድረግ ኢሳያስን እንደሞዴል የወሰዱም አሉ። ይህ ሰጥቶ ለመቀበል የሚደረግ ጨዋታና “የፖለቲካ ስህተት ላለመፈጸም” ካልሆነ በስተቀር መሬት ላይ ያለው እውነታ የሚያሳየው ሌላ ነው። በኢሳያስ አፈወርቂ ውስጥ የኤርትራን ህዝብ እናያለን። ተለይቶ ያለ፣ ከሌላው አለም የራቀ፣ የተቆሳቆለና ተስፋው የጨለመበት ሰው። እሳቸው የሚመሩት ህዝብ ነጸብራቅ ናቸው።

ኤርትራ አሁን ለደረሰችበት ደረጃና ለገባችበት ቀውስ ማንም ውጫዊ አካል ሊወቀስ አይችልም። ራሱ ስርዓቱ ያመጣው መከራ ነው። ከ99.9 በመቶው ተረት-ተረት ሪፈረንደም በኋላ ነጻ አውጪው ሻዕቢያ በአለም ላይ ታይቶ ያማይታወቅ አዲስ ስርዓት አሰተዋወቀ። ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈጻሚና ህግ ተርጓሚው አንድ ነው። ህጉም አንድ ሰው ነው። የብዙሃን ፓርቲ ፓርላማ በህግ የተከለከለበት ሃገር።  ፕሬስ የሌለው መንግስት፣ ፍትህ እና ፍትሃዊ ስርዓት የሌለው ስርዓት። … ይህ አዲስ አይነት ስርዓት የህዝቡን ህይወት የለወጠ ቢሆን ኖሮ፤ እንደተባለውም ኤርትራን የአፍሪካ ሲንጋፖር ያደረገ ቢሆን ኖሮ፣ እንደ ሞዴል ሊወሰድ ይችል ነበር። እውነቱ ሌላ ነው። ህዝበ ኤርትራ ምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ የቢቢሲን ያለፈው ሳምንት ዘገባ መመልከቱ ብቻ ይበቃል። የዊኪሊኩ ጁልያን አሳንጅ የለቀቀው አንድ ኬብል ላይ ህጻናት እንኳን በኤርትራ መንግስት ምን ያህል እየተሰቃዩ እንደሆነ ዘርዝሮታል።

እኝህ አንባገነን ሰው ዘንድ ሄዶ ጥያቄ የሚጠይቅና የሚጋፈጥ ጋዜጠኛ የሚደነቅ ነው። ህግ፣ ፍትህ፣ ዲፕሎማሲ ምናምን የሚባሉ ነገሮች የማይገባው ሰው ዘንድ ሄዶ ለመነጋገር መወሰን ቀላል አይሆንም። ይህን ስል ያለ ምክንያት አይደለም። ትውልደ ኤርትራዊው የስዊድን ዜጋ፣ ጋዜጠኛ ዳዊት ኢስኃቅ ድንገት ተይዞ ወዳልታወቀ ስፍራ ከተወረወረ 15 ዓመት ሞላው። ጋዜጠኛ ዳዊት የት እንዳለ እስካሁን አይታወቅም። በኤርትራ ዛሬ 20 ሺ የፖለቲካ እስረኞች በየእስር ቤቱ እንደታጎሩ የአምነስቲ ዘገባዎች ይጠቁማሉ። በኢሳያስ የግል እስር ቤት ውስጥ ከነበሩት 35 የቀድሞ ከፍተኛ ባለሥልጣናት መካከል 15ቱ በስቃይ ህይወታቸው አልፏል። በ“አደርሰር”፣ በ“አጂፕ”፣ በ“ኢራኢሮ” እና በ”ጋልዓሎ” እስር ቤቶችና በኮንቴይነሮች ታጉረው እየሞቱ ያሉት ቁጥር ጥቂት አይደለም። የምእራቡ አለም የዲሞክራሲ እሴቶች ከኤርትራ መዝገበ-ቃላት ተፍቀው እንዲወጡ ተደርጓል። በዚህ የፖለቲካ አየር እኝህ ሰው ፊት ቀርቦ የሚጎረብጡ ጥያቄዎችን ማንሳት በራስ መፍረድ ነው።…

ባየር ላይ የሚነገሩ በርካታ ጉዳዮች በቃለ-ምልልሱ ተነስተዋል። የመቶ አመት የቤት ስራው ጉዳይ ተነስቷል። ህገመንግስቱን ከሌንጮ እና ከመለስ ጋር የማርቀቁ ጉዳይ ተነስቷል። ከህብረብሄራዊ ድርጅቶች ይልቅ የዘር ድርጅቶችን ብቻ የመደገፋቸው ጉዳይም ተነስቷል።

ምላሻቸው ግን ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ሆነብን። አጠር ብለው ሲቀርቡ ይህን ይመስላሉ።

ጥያቄ፣ “ትውልድዎ እና እድገትዎን ይንገሩን?”

መልስ፣ “የትግሉ ውጤት ነኝ።”

ጥያቄ፣ “ስለጤናዎ ሁኔታ ይንገሩን “

መልስ፣ “እድለኛ ነኝ… ጠላት እንደሚያወራብኝ አይደለሁም።”

ጥያቄ፣ “በዘር የተደራጁ ሃይሎችን ነጥለው ለምን ይደግፋሉ?”

መልስ፣ “ሻእቢያ ድርጅት አቋቁሞ አያውቅም።”…..

እያለ ምላሻቸው ከጥያቄው ጋር አራምባና ቆቦ ሆነብን። የማይመቹ ጥያቄዎችን እንደቀልድ ያልፏቸውና ሌላ ታሪክ ሊነግሩን ይሞክራሉ። በመጨረሻ ግን ላሽ እያሉ ያለፏቸው ጥያቄዎች ላይ ጠቅለል አድርገው ምላሽ የሰጡ ይመስላል።

“..ያለፈውን እንተወው እና ወደፊት ምን ማድረግ ይገባናል የሚለው ላይ ማተኮር ነው ያለብን።” ሲሉ ምክር ሰጥተዋል። ይህች መልዕክት የቃለ-ምልልሱ ቁልፍ ትመስላለች። አስቀድመው “ባለፈው በሆነው በአንዳቸውም ነገር አንጸጸትም።” ብለውማል።

ከዚህ ቀደም ከኤልያስ እና ስለሺ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ያሉትንም እናስታውስ። “የራስን እድል በራስ መወሰን እስከመገንጠል የሚለው አንቀጽ በሕገ-መንግስቱ ውስጥ መጨመር ስህተት ነው።” ብለዋል። ራሳቸው ከቀድሞ ወዳጆቻቸው ጋር ሆነው ያረቀቁትን ሰነድ ነው ስህተት መሆኑን የነገሩን። ይህ ነገር ስህተት ከሆነ ታዲያ የሰራነው ስህተት የለም ብለው ለምን ይዋሻሉ? እንደሚባለው የአልዛይመር ችግር ይኖርባቸው ይሆን?

እርግጥ ነው። ስለ ኢሳያስም ሆነ ስለ ኤርትራ ጉዳይ እኛ አያገባንም። አምባገነንነታቸው የኛ ጉዳይ ላይሆን ይችላል። የዚያች ሃገር ጉዳይ “ኢትዮጵያዊ አይደለንም” ብሎ 99.9 በመቶ ድምጽ የሰጠው ህዝብ ጉዳይ ነው። ግና ባሰኛቸው ጊዜ እየተነሱ ቁስላችንን ሲነካኩብን ዝም የማለት ሞራል አይኖረንም። ከአሰብ በግፍ እና በአሰቃቂ ሁኔታ ተፈናቅለው ሲያበቁ መስቀል አደባባይ ለወራት የፈሰሱ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ከቶውንም ከአእምሯችን አይጠፋም። ኢሳያስ አፈወርቂ ዛሬ በሰራነው አንጸጸትም፣ እንዲያውም ካሳ ይገባኛል ሲሉ በድፍረት ተናገሩ። ምን እንላለን? በወገኖቻችን ላይ እየሰሩ ላሉት ግፍ ፈጣሪ ይከፍላቸዋል። ካሳቸውንም ከታሪክ መዝገብ ያገኙታል።

በፖለቲካ ቋሚ ጠላት ወይንም ቋሚ ወዳጅ የለም። የጋራ ጥቅም ግን አለ። ሰጥቶ መቀበል የሚሉት ነገር። ኢሳያስ አፈወርቂ ግን ለጋራ ጥቅም ሳይሆን ለጽድቅ እንደሚሰሩ አይነት ነው እየነገሩን ያሉት።  በኢትዮጵያ ችግሮች አሉ። አማራጭ የፖለቲካ በሮች በሙሉ ተዘግተዋል። አገዛዙ ፍጹም አንባገነን ሆኗል። ኤርትራን መጠጋት እንደ መፍትሄ የወሰዱ ወገኖች ሌላ የትግል አማራጭ ስላጡ ሊሆን ይችላል። የቸገረው እርጉዝ ያገባል እንደሚባለው። ያለፉት ተመክሮዎች ግን ሻእቢያን በጥርጣሬ እንድናይ ያደርገናል።  ከአስር አመት በፊት አስመራ የመሸጉ ሃይሎች አሁንም አስመራ ላይ ናቸው። አንዳንዶቹ እዚያው ሲያረጁ ሌሎቹ  ደግሞ አእምሯቸውን ስተው ሲለቅቁ  እያየን ነው። የእነ ኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ  ደብዛ መጥፋት፣ 18 የአርበኞች ግንባር አባላት በድንገት መሰወር፣ አስመራን እንዳይለቅቁ እገዳ የተጣለባቸው የተቃዋሚ ሃይል አባላት… ወዘተ እጣ ፈንታ በኢሳያስ እጅ ላይ ነው ያለው። ስለ ኢትዮጵያ መቆርቆር ከዚህ ይጀምራል። እነዚህ ወገኖቻችንን ነጻ ካደረጓቸው በኋላ ኢትዮጵያውያንን ለውይይት ቢጠሩ አንድ ነገር ነው። በትንሹ ያልታመነ፣ በትልቁ አይታመንምና።

ቀድሞ “ከኤርትራ ውጭ ነጻነት ላሳር!” ብለው የነበሩ ሃይሎች አሁን ላይ ሆነው “ተሳስተናል!” እያሉን ነው። ለዚያውም በምሬትና በጥላቻ። ታዲያ ችግሩ የት ነው ያለው? ከተቃዋሚዎቹ ወይንስ ከሻዕቢያ? መልስ የሚሻው የብዙዎች ጥያቄ ነው።

The post ኢሳያስ አፈወርቂን በጨረፍታ (ክንፉ አሰፋ) appeared first on Zehabesha Amharic.

አድዋን ስንዘክር፡ –ማተቤ መለሰ ተሰማ

$
0
0

Battle of Adwaአስደናቂ ለሆነ የረጅም ዘመን አኩሪ ታሪክ ባለቤት የሆነችው፡ እናት ሃገራችን ኢትዮጵያ፡ ከ1762 እስከ 1845 ዓ.ም ድረስ በነበረው 70 አመት ጊዜ ውስጥ፡ በዘር ባይሆንም ልክ እንደዛሬው፡ ልጆቿ ተከፋፍለው፣ ልማትና ብልጽግናዋ ተገትቶ፣ ለሁለንተናዊ ውድቀት የተዳረገችበት ወቅት ነበር።

እጅግ በጣም የሚገርመው ደግሞ፡ ለዚያ ውድቀት የዳረጋት፡ የትግራዩ ተወላጅ እራስ ስዑለ ሚካኤል፡ አማቱንና በወቅቱ የነበሩትን ንጉስ አጼ ኢዩአሰን በቤት አሽከሮቻቸው አሳንቆ በማስገደሉ ነበር።

34

ማተቤ መለሰ ተሰማ

እንግሊዝ አጼ ቲዮድሮስ፡ ያሰሩባትን ዜጎቿን እነ ቆንሲል ካሜሮንን፡ በሃይል ለማስፈታት፡ ወደ ኢትዮጵያ ጦሯን በላከች ጊዜ፡ በሮቤርት ናፒር የሚመራው ወራሪው ጦር ከምጽዋ ዙላ፣ ከዙላ ሰናፈ፣ ከሰናፈ አሸንጌ፣ ከአሸንጌ ሙጃ፣ ከሙጃ መረዋ፡፡ በማረፍ እየተዝናና እና መንገድ እየሰራ ሚያዚያ 2 ቀን 1860 ዓ.ም. በሸሎ እሰኪደርስ ድረስ፡ መንገድ በመምራትና በመንከባከብ አምጥተው፡ የእኒያን ብሄራዊ ጀግና፡ የአጼ ቲዮድሮስን እልፈተ ህይወት ያፋጠኑት፡ አሁንም የትግራዩ ተወላጅ፡ ካሳ ምርጫ፡ ወይንም በንግስና ስማቸው አጼ ዩሃንስ እንደ ነበሩም ይነገራል። ምንም እንኳን በሗላ ከወራሬ ጋር ሲፋለሙ በክብር ቢወድቁም።

ዛሬ በምናሰበው በ1888 ዓ.ም አድዋ ላይ በተካሄደው፡ የኢትዮጵያና የኢጣልያን ጦርነት ጊዜ በእራስ መኮንን የሚመራው ቀዳሚ ጦር። አምባላጌ እንደደረሰ ገና መሬት ሳይዝ በወጊያ የጠመዱትም የትግራይ ተወላጅ ባንዳዎች ናቸው።

በ1928 ዓ.ም በሁለተኛው የኢጣልያ ወረራ ወቅት፡ አርበኛው ፊትለፊ ከጠላት ጋር ሲፋለም፡ በትግራይ በቀሉ ባንዳ በደጃዝማች ሃይለስላሴ ጉግሳ፡ የሚመራው የትግራይ ተወላጆች ስብስብ፡ ተመሳስሎ በጀርባ እየገባ ያልተጠበቀ አድጋ በማድረስ፡  ለሽንፈታችን ትልቅ አስተዋጽኦ ከማድረጉም በላይ፡ ሲሸሽ እየተከታተለ የደከመውንና ቁስለኛ ወንድሙን በመግደል፡ ከኢጣልያን የከፋ በርካታ የኢትዮጵያን አርበኛ ፈጅቷል።

ሀምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም. አቡነ ጴጥሮስ አዲስ አበባ ላይ ሲረሸኑ፡፡

ህዳር24ቀን 1929 ዓ.ም. አቡነ ሚካኤል ጎሬ ላይ ሲረሸኑ፡፡

የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. በግራዞያኒ ትእዛዝ አዲስ አበባ ላይ ከ30 ሺህ የማያንስ ህዝብ ሲጨፈጨፍ፡፡ ትዕዛዝ ፈጻሚዎቹ  አሁንም ትውልደ ሰሜን ወንድሞቻችን  ነበሩ።

1969ዓ.ም ሶማሌ ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅትም፡ ወያኔ መቃድሾ ከተማ ቢሮ ከፈቶ፡ በተለይ በሰራዊታችን ውስጥ የእሱን ሰው አሰርጎ በማስገባት፡ ለጠላት መረጃ ከማቀበል ጀምሮ፡ የሶማሌ የስለላ ማዕከል፡ የኢትዮጵያ ጦር ግንኙነት የሚያደርግበትን፡ ሬዲዮ እየጠለፈ ሲያቀርብለት በመተርጎም፡ ለሶማሌ ሰራዊት እየሰጠ በኢትዮጵያዊያን ላይ ጉዳት እንዲደርስ በማድረግ ትልቅ ክዕደት ሲፈጽም ነበር።

በአብዛኛው ማለት በሚያስደፍር ሁኔታ፡ በሃገራችን ላይ ወረራ በተሰነዘረ ቁጥር በርካታ የትግራይ ተወላጆች፡ ከጠላት ጎን በመሰለፍ የእናታቸውን ጡት ሲነክሱ ለመኖራቸው ድርሳናቶቹ ሁሉ ቁልጭ አድርገው ያመላክቱናል።

ዛሪም ታሪክ እራሱን ደገመና፡ ትግራይ የፈለቁ ጉዶች ናቸው፡ እኛን በዘርና በሃይማኖት ከፋፍለው፡ ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር እንደምስራቅ ጀረመንና እንደ ዩጎዘላቢያ ከዓለም ካርታ እንድትፋቅና እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ በማለት አፍ ሞልቶ ደረት ነፍቶ የሚናገር ዜጋ እንዳይኖር 24 አመት ሙሉ ሽንጣቸውን ገትረው በመስራት ላይ ያሉት።

ይህንን ስል ግን ትውልደ ትግራይ ሆነው፡ ለአገር አንድነትና ለወገን ነጻነት፡ የተጋደሉ አልነበሩም። አሁንም፡ የሉም እያልሁ አይደለም። ትናንት እነ አሉላ አባነጋን፣ እነ እራስ ስዩም መንገሻን፣ እነ ደጃዝማች አርያን እነ እራስ መነገሻ ስዩምን፣ ወ.ዘ.ተ. ዛሪም የትግራይ ዲሞክራሴያዊ ንቅናቄ ሰዎችን በተለይም የድርጅቱ መሬ የነበረውንና አሁን በህይወት የሌለውን ፍስሃ ሃይለማርያምን የመሰለ የሃገር

2.. ፍቅር ያንገበግበው የነበረውን። እነ ገብረመደህን አርያን፣ እነ አብርሃ በላይን፣ እነ አብረሃ ደስታን፣ እነ አስራት አብርሃምን ያፈራች ስለሆነ።

መነሻዬ የኢትዮጵያን ታሪክ፡ ወይንም የትግራይ በቀል የጥፋት መልክተኞችን ጉድና ሁላችንም ተደራሲዎች የሆንበትን፡ የወያኔን መግለጫ ቃላት መለኪያ መስፈርት የማይገኝለትን፡ የግፍ ክምር እየናድሁ የምታውቁትን በመድገም ጊዜያችሁን ለማባከን አስቤ አይደለም።

ይልቁንም በትግራዩ ተወላጅ፡ በእራስ ስዑለ ሚካኤል፡ መሰሬ ተንኮል ተበታትና የነበረችዋን ኢትዮጵያን፡ እምዬ ምኒልክ። እንዴት መልሰው እንደገነቧት በአይነ ህሌናችሁ ወደሗላ እንደትመለከቱ ለማነሳሳትና ለውይይት ሃሳብ ለማጫር  የተጠቀምሁበት ነው እንጅ።

ወደዛሬው ምልከታየ ስገባ።

አጼ ምኒልክ ነሃሴ 12 ቀን 1836 ዓ.ም በሽዋ ክፍለ ሃገር በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አንጎለላ ኪዳንምህረት ተወለዱ። ከ12 አመት እድሜያቸው ጀምሮ በግዞትም፣ በማደጎም፣ በአማችነትም ከአጼ ቲዮድሮስ ቤት አደጉ።

ከእድገታቸው እስከ ንግስናቸው ያለውን ታሪክ ለጊዜው ላቆየውና። ከነገሱ በሗላ በተለይም ከዛሬው መሰባሰቢያችን ጋር በቀጥታ የተያያዘውን ከፋሽትት ኢጣልያን ወራሬ ጦር ጋር ያደረጉትን ተጋደሎ ባጭሩ ልጥቀስ።

እምዬ ምኒልክ መላዋን ኢትዮጵያን ከማስረዳደራቸው በፊት። የሽዋ ንጉስ በነበሩበት ወቅት ከኢጣልያን መንግስ ጋር ወዳጅ በመሆናቸው እስከ መሳሬያ እርዳታ ድረስ ያገኙ ነበር። በሗላ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ሲሆኑ ግን። ኢጣልያን  ኢትዮጵያን ለመውረር በነበራት ፍላጎት መሰረት በአጼ ዩሃንስ ጊዜ የጀመረችውን ወረራ እያሰፋችና  እየገፋች ስትመጣ። በምኒልክና በኢጣልያን መንግስት መካከል የቆየው መልካም ግንጉነት እየሻከረ ሄደ።

አጼ ምኒልክ ከኢጣልያን ጋር የነበረው ወዳጅነታቸው እንዲቀጥል አጥብቀው  ቢጥሩም። በኢጣልያን በኩል ግን ተቀባይነት አላገኙም ነበር። በተለይም የውጫሌ ውል እየተባለ በሚጠቀሰው አንቀጽ 17 ላይ በኢጣልያነኛ የተጻፈው ሃገራቸውን እንደሚጎዳ ሲገነዘቡ ክተት ሰራዊት ምታነጋሬ በማለት የሚከተለውን ጥሬ ለመላው ኢትዮጵያ ህዝብ አስተላለፉ።

የአጼምኒልክ ጥሪ ሙሉ ቃል

እግዚያብሄር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ። እኔም እስካሁን በእግዚያብሄር ቸርነት ገዛሁ። እንግዴህ ሞት ለሁሉ ነውና ብሞትም በእኔ ሞት አላዝንም። ደግሞ እግዚያብሄር አሳፍሮኝ አያውቅም። ከእንግዴህም ያሳፈረኛል በዬ አልጠራጠርም።

አገር የሚያጠፋ፣ ሃይማኖት የሚለውጥ፣ ጠላት እግዚያብሄር የወሰነልንን የባህር በር አልፎ መጧል። እኔም የሃገሬን ከብት ማለቅ የሰውንም መድከም አይቸ ዝም ብለው እያለፈ እንደፍልፈል መሬት ይቆፈር ጀመር። አሁን ግን በእግዚያብሄር እረዳትነት ሃገሬን አሳልፊ አልሰጥም።

የሃገሬ ሰው ከአሁን በፊት የበደልሁህ አይመስለኝም። አንተም እስካሁን አላስቀየምከኝም። ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ። ጉልበት የሌለህ ለልጅህ፣ ለሚስተህ፣ ለሃይማኖትህ ስትል በሃዘን እርዳኝ። ወስልተህ የቀረህ ግን በሗላ ትጣላኛለህ። ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም። ዘመቻየ በጥቅምት ነውና የሽዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ወረኢሉ ከትተህ ላግኝህ።

የጥሬው መጨረሻ።

በማለት ካዘዙ በሗላ በእራስ መኮነን የሚመራውን ቃፊር ጦር አስቀድመው እሳቸው ህዳር 2 ቀን 1888 ዓ. ም ከአዲስ አበባ በመነሳት ወደ ሰሜን አመሩ።

ንጉሱ በመንገድ ላይ እንዳሉ በራስ መኮነን የሚመራው ቀዳሚ ጦር አምባላጌ ደረሰ። በዚህ ወቅት የኢጣልያን ጦር። የኢትዮጵያን ጦር ከመንግድ እንደመጣና እንደደከመ እንደገናም ቦታ ሳይዝ። ለመምታት ተዘጋጅቶ ቅድም እንዳልኩት በርካታ ትግራይ በቀል ባንዳዎችን በማሰለፍ ውጊያ ከፈተበት። ግን ከ6 ስአት በላይ በፈጀው ጦርነት። ኢጣልያን የመጀመሬያውን የሸንፈት ጽዋ። በእራስ መኮነን ጦር ተጎነጨና ከአምባላጌ ምሽጉ ተባበረ።

አጼምኒልክም ታህሳስ 29 ቀን 1888 ዓ.ም መቀሌ እንደደረሱ። አዚያ ሰፍሮ የነበረውን የጠላት ጦር ዙሬያውን በማስከበብ የሚጠጣው ወሃ ከማሳጣታቸውም በላይ። በውጊያም መድረሻ ስላሳጡት

3.

ያለቀው አልቆ የተረፈው የሃገር ሽማግሌዎችን አማላጅ በመላኩ መንገድ ተከፍቶለት ወደ አዲግራት ሸሸና ለሁለተኛ ጊዜ ሽንፈቱን አጣጣመ።

በዚህ ዘመቻ በኢትዮጵያ በኩል የተሰለፈው ሰራዊት። መቶሽህ እንደሚደርስ የሚገመት ሲሆን። ከዚህ መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆነው አርበኛ ጦርና ጎራዴ ብቻ የታጠቀ እንደነበርና ጠብመንጃ ያለውም ቢሆን ጠላት ከታጠቀው ዘመናዊ መሳሬያ ጋር ሲነጻጸር የሰማይና የመሬት ያህል የተራራቀ እንደነበር የታሪክ ጸሃፍት ያሰምሩበታል።

በዚህ ጦርነት በኢትዮጵያ በኩል የተሰለፉ ዋና ዋና የጦር አዝማቾች።

  1. እትጌ ጣይቱ ብጡል፡

2.ንጉስ ተክለ ሃይማኖት፡

3.ፍታውራሪ ገበየሁ፡

4.ደጃዝማች ጫጫ፡

5.እራስ መኮንን፡

6.እራስ መንገሻ ስዩም፡

7.እራስ መንገሻ አቲከም፡

8.እራስ ሚካሌል፡

9.እራስ ወሌ ብጡል፡

10.ደጃዝማች በሻህ አቡዬ፡

11.እራስ ጉግሳ፡

12.እራስ አሉላ አባነጋ፡

13.ዋግሹም ጓንጉል፡

14.እራስ ወርቄ  የተባሉት ነበሩ።

በኢጣልያን በኩል የጦር አዛዦች ደግሞ፡

  1. ጠቅላይ አዛዡ ሌትና ጀሪናል ባራቲይሪ፡
  2. ጀኔል ዦሴፔ ኦሪሞንዱ፡
  3. ጀኔራል አማኑኤል ደቦርሜዳ፡
  4. ጀኔራል ማቲዮስ አልቤርቶኒ፡
  5. ጀኔራል ዦሴፔ ኤሌና፡
  6. ኮሎኔል ቫሊንዞኖ፡ ነበሩ።

በዚህ የሃይል አሰላልፍ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ልክ የዛሬ 119 አመት ከሌሊቱ በ11 ስአት በኢጣልያን ተንኳሽነት  አድዋ ላይ ወሳኙ ጦርነት ተከፈተ።

ሊነጋጋ ሲል ከሌሊቱ በ11 ስአት የተጀመረው ጦርነት። ቀኑን ሙሉ ውሎ ከሌሊቱ 5 ስአት በኢትዮጵያ አሸናፊነት ተጠናቀቀና ሃገራችን ኢትዮጵያ በጥቁር አንበሶች ልጆቿ አጥንት ክስካሽና ደም ፍሳሽ ሃያልነቷ በአም ሁሉ ተናኘ።

ውጤቱም የአለም ህዝብን  አስደነቀ። የጀግኖች አባቶቻችን አይበገሬነትም በማያጠራጥር ሁኔታ ታወቀ።  በኢጣልያን በኩል ከተሰለፉት የጦር አዛዦች መካከል ከጠቅላይ አዛዡ ከሌትና ጀኔራል ባራቲይሪ በቀር ሌላው የጦር አዛዥ ጀኔራልና ከፍተኛ መኮንን በሙሉ ተደመሰሱ።

በኢጣልያን በኩል ከተማረከውና ቆስሎ ከሸሸው ሌላ 9215 ተዋጊ ሲሞት። ከኢትዮጵያ 7000 ሰው ሞቷል። ከዚህ ውስጥ ከወገን የሞቱ አዋጊዎች።

  1. ደጃዝማች በሻህ አቡዬ፡
  2. ደጃዝማች ጫጫ፡
  3. ፍታውራሪ ገበየሁ፡
  4. ፍታውራሪ ተክሌ፡
  5. ቀኛዝማች ታፈሰ አባይነህ፡
  6. ፍታውራሪ ዳምጠው፡
  7. ደጃዝማች ማናዬ፡

4.

  1. ፍታውራሪ ወልደ ሚካሌል።
  2. ቀኛዝማች ተገኘወርቅ፡
  3. ፍታውራሪ አምባዬ።
  4. ቀኛዝማች ተሰማ ወልዴ፡
  5. ፍታውራሪ ሸንኮሩ፡
  6. ባላንበራስ በለው፡

14.ባላንበራስ አደራ ወ.ዘ.ተ. ይጠቀሳሉ።

ማጠቃለያ

በጣም የሚገርመው የአውሮፓ ሃያላን መንግስታት። አፍሪካን በቅኝ ለመግዛት። እንደ ቅርጫ ስጋ የተከፋፈሉበትና። እርስ በርስ ላለመነካካት የተፈራረሙት የካቲት 26 ቀን 1877 ዓ.ም ከአድዋ ጦርነት ከ3 አመት በፊት ሲሆን። በክፍፍሉም።

1ኛ. እንግሊዚ፡ ግብፅን፣ ሱዳንን፣ ናይጀርያንና ኬንያን።

2ኛ. ፈረንሳይ፡ ምህራብና ሰሜን አፍሪካን።

3ኛ. ፖርቱጋል፡ አንጎላንና ሞዛቢክን።

4ኛ. ጀርመን፡ ታንዛንያንና ቶጎን።

5ኛ. ቤልጅም፡ ኮንጎን።

6ኛ. ኢጣልያን፡ሶማልያንና ሊብያን ወ.ዘ.ተ በማድረግ ሲከፋፈሉ።

ኢትዮጵያን አልነኳትም ነበር። ምክናያታቸውም የረጅም ዘመን የተጠናከረ መንግስትና። አይበገሬ ህዝብ  እንዳላት ስለሚያውቁ።  እንደሆነ ይነገራል የተጨበጠ ማስረጃ ባይኖርም።

ዛሪስ በእኔና እናንተ ድርሻ። ሃገራችን ኢትዮጵያ በዓለም ህዝብ ዘንድ የነበራትን ክብር እንዳስጠበቀች ነች ወይ? የሚል ጥያቄ  ቢነሳ ሁላችንንም የሚያስማማን መልስ። አይደለም የሚለው እንደሚሆን አልጠራጠርም። ለምን? ከተባለ ልንሰጠው የምንችለው ምላሽ ግን የተለያየ እንደሚሆን እገምታለሁ።

በበኩሌ የእኔና የእናንተ ትውልድ ፈጹም እራስ ወዳድ ስለሆነ። ሌላው ሞቶለት እሱ ተጠቃሚ መሆንን ስለሚያሰላ ነው የሚል ነው ።

እናንተስ በእኔ ሃሳብ ትስማማላችሁ? አይደለም ሌላ ምክናያት ስላለ ነው ወኔ የከዳን የሚል ካለ ለመስማት ዝግጁ ነኝ። መልካም ውይይት እያልሁ እንደ እናንተው ቁጭ ብዬ የግል አስተያይቴን መሰንዘር እችል ዘንድ ዝግጅቴን በምትከተለዋ አጭር የግጥም ስንኝ ልቋጭ።

እርዕሷንም አድዋ ብያታለሁ!!

አድዋ

ከሰሜን ከደቡብ ከመግቢያና መውጫ፣

ከምስራቅ ከምእራብ ከሉም አቅጣጫ።

ቋንቋ ሳይለያቸው ዘር ማንዘር ሳይቆጥሩ፣

አማራ ኦሮሞ በማለት ሳይጠሩ፡

በዚያች የቁርጥ ቀን ቀድመው የደረሱ፣

ጥንት አባቶቻችን እነዝናር ልብሱ፡

ምሳሌ በመሆን በኩራት ሲጠሩ፣

ከመቃብር ጀርባ ዝንታለም ሊኖሩ፣

በአድዋ መልካ ላይ ታሪክን የሰሩ።

አባቶች ነበሩን የሃገር መከታ፣

ህይወት የሚሰጡ በመሆን አለኝታ።

እጅ ለእጅ ተሞሻልቀው በታጠቁት ካራ፣

ፈንጥቀው ያአለፉ እንደ ንጋት ጮራ።

ምኒልክ ለአድዋ ባቀረቡት ጥሪ፣

ያች ጣይቱ ብቱል ሆነች የጦር መሬ።

አዎ!! አድዋ!! አድዋ!! አድዋ!!

5.

የዛሬ ማፈሪያ የትናንት መኩሪያዋ፡

የዛሬ ማፈሪያ የትናንት መኩሪያዋ።

አመሰግናለሁ፡

ማተቤ መለሰ ተሰማ

በ2007 የ119ኛው የአድዋ የድል ባል በኖርዌይ የኢትዮጰያ ማህበር ሲያከብር የቀረበ የውይት መነሻ።

The post አድዋን ስንዘክር፡ – ማተቤ መለሰ ተሰማ appeared first on Zehabesha Amharic.


ከጨርቁና ከቋንቋው በስተጀርባ –ይሄይስ አእምሮ (ከኢትዮጵያ)

$
0
0

ዛሬ እሁድ የካቲት 22 ቀን 2007 ዓ.ም የወያኔ 40ኛ ዓመት ክብረ በዓል መዘምዘሚያ በወያኔው አባል በቱጃሩ አላሙዲን የሚሌኒየም አዳራሽ ውስጥ እየተከበረ ነው፡፡ ዘፈንና ደስታ አለቅጥ ሲበዛ የሚያስከትለውን ምልኪያዊ ሀዘን የተረዱ አይመስሉም፡፡

እኔ እንዳለመታደል ሆኖ የወያኔን ሚዲያ አልከታተልም – በሌላ ምክንያት ሣይሆን ለጤንነቴ ቅድሚያ ከመስጠት አኳያ ነው፡፡ ነገር ግን የሚከታተሉ ሰዎች ብዘውን ጊዜ  ምን እንደተላለፈ በመጠጥ ቤትና በሕዝብ መገናኛ ሥፍራዎች ይነግሩኛል፡፡ መስማት ባልፈልግም ጆሮየን መጠቅጠቅ አልችልምና እሰማለሁ፡፡ የዛሬውን አስደናቂ ወሬ የሰማሁት እንግዲህ ወድጄ ሳይሆን ተገድጄ መሆኑ ነው፡፡

የወያኔ በዓል በትግራይ ውስጥ ከሁለት ወራት ላላነሰ ጊዜ በትግርኛም እንዳስፈላጊነቱ በዐማርኛም ተከብሯል፡፡ በመሠረቱ ወደ ስድስት ሺህ ገደማ በሚገመቱት የዓለም ቋንቋዎች ቢከበርም ግድ አይሰጠኝም ብቻ ሣይሆን የምከፋ አይደለሁም፡፡

ሰዎች እየተዘባበቱና በወያኔ እየቀለዱ ሲናገሩ እንደሰማሁት ደብረጽዮን የሚባለው የወያኔ ባለሥልጣንና ቱባ ካድሬ በዚህ የሚሌኒየም አዳራሽ የበዓሉ መዝጊያ ሥነ ሥርዓት ላይ ያደረገው ንግግር ሙሉ በሙሉ በትግርኛ ነው አሉ፡፡ እርግጥ ነው – በሕወሓት በዓል ላይ ሌላ ቋንቋ እንዲነገር መጠበቅ አግባብነት ላይኖረው ይችላል፡፡ መሠረታዊ ችግሩ ግን የአንድ ፓርቲ ወይም የነፃነት ግምባር የመላ ሀገሪቱን ሕዝብ እንደነሱው አጠራር ‹ሕዝቦች› ንብረት የሆነውን ሚዲያ በጉልበት አስገድዶ – ፕሮግራሞቹንም ሁሉ አስቁሞ – ለግል ጉዳዩ ማዋሉ ነው፡፡ ይህ ማንአለብኝነት ነገና ከነገ ወዲያ በታሪክም በወንጀልም የሚያስጠይቅ ትልቅ ጥፋት ነው፡፡ እስካሁን ባለው ሁኔታ ሌሎች “አቻ” ፓርቲዎች ወይም የ“ነፃነት ንቅናቄዎች” – ለምሣሌ እንደ ኦህዲድና ብአዴን እንዲሁም ደኢሕዲን የመሳሰሉት –  ይህን የመሰለ በጣም የተራዘመ ደማቅ ሀገራዊ የመገናኛ ብዙኃን ሽፋን፣ የገንዘብ መዋጮና “መንግሥታዊ” የበጀት ድጋፍ አላገኙም – ከአሁን ወዲያም ቢሆን ፍትሃዊ የድርጅቶች እኩልነት በተግባር እንዲታይ ወያኔዎች የሚፈቅዱ ከሆነና ሕወሓት እስከመጋቢት ድረስ የሚቆይ ከሆነ የፊታችን መጋቢት 17/2007 እንደሚከበር የሚጠበቀው የኦህዴድ የምሥረታ ወይም ከደርግ ምርኮኛ ብሔራዊ ዘማቾች በወያኔ ተጠፍጥፎ ለመናጆነት የተሠለፈበት በዓል በምን አኳኋን እንደሚከበር ለማየት በጉጉት እንጠብቃለን፡፡ ከህዝብ ብዛት አንጻር ወያኔ ትንሽ የመቶኛ ሥሌት ይዞ ሳለ በዚህ መልክ በዓሉን ማክበሩ ሀገሪቱንና ሀብቷን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥሩ ሥር ማድረጉን ያመለክታል የሚል ግምት ያስጨብጣል፡፡ ይህ አካሄድ ሀብቷን ብቻ ሣይሆን ከወያኔ በእጅጉ እንዲያውም በፍጹም ሊወዳደር በማይችል ሁኔታ ኆልቁ መሣፍርት የሌለው የሕዝብ ቁጥር ይወክላሉ የሚባሉ “አቻ” ግምባሮችንና ንቅናቄዎችን እንዲሁም ውዝዋዜዎችን በእግሩ ሥር አውሎ እንደፈለገው እየተጫወተባቸው መሆኑን ይጠቁማል – እንደአካሄድ፡፡ ይህ ደግሞ በተለይ በጥገኛ ድርጅቶች ዘንድ ታላቅ የሀፍረት ምንጭ ሆኖ በታሪክ የሚመዘገብ ይመስለኛል፡፡

ባለራዕዩ መሪ ሙትቻው ሟች መለስ ዜናዊ አንድ ወቅት ስለ ሰንደቅ ዓላማ ሲጠየቅ – መጥቀስ ይቻላል –  “ባንዲራ ጨርቅ ነው፡፡ ምሥጢሩ ያለው ከባንዲራው በስተጀርባ ነው” ብሎ ነበር፡፡

መለስ በዚህ ንግግሩ ብዙ ተተችቷል፡፡ እንደኔ ግን ትክክል ነበር፡፡ ሰንደቅ ዓላማ ከጨርቅ ውጪ ከብረት ወይም ከእንጨት ተሠርቶ ሲውለበለብ አይቼ አላውቅም – እናም ከዚህ እሳቤ አንጻር መናገር ፈልጎ ከሆነ ስህተት አልነበረውም፡፡ ችግሩ የሚመስለኝ ከአመለካከትና ከንግግሩ በስተጀርባ ካለው ፍላጎት ነው – እንግሊዝኛ ተናጋሪዎቹ “intention” የሚሉት፡፡ እንደሚመስለኝ እርሱ ማለት የፈለገው “ሕወሓት ለ‹ሀገሪቱ› የፈጠረላት ባንዴራ ከጥንቱ ባንዴራ የተለዬ ነው፡፡ የጥንቱ ባንዴራ ብሔር ብሔረሰቦችንና ሕዝቦችን በኃይል ጨፍልቆ የግዛት አንድነት ለመመሥረት የሚጥርን ሥርዓት የሚወክል ሲሆን አዲሱና እኛ ሕወሓቶች የሠራነው ባንዴራ ግን የሀገሪቱ ዜጎች በፈቃደኝነት ላይ በተመሠረተ ሁኔታ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ፈጥረው የሚኖሩበትን ፍትሃዊ ሥርዓት የሚወክል ነው፡፡ ስለሆነም የጥንቱ ባንዴራ ከጨርቅነት ያለፈ ትርጉም ስለሌለው ከጨውና ስኳር መቋጠሪያነት ባለፈም ተቀዳዶ ቢጣልና ቢቃጠልም ሲያንሰው ነው” ነው፡፡ መለስ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ እንደማይወድ እንዲያውም እንደአባቱ ገዳይ ያህል እንደሚጠላው የታወቀ ነው፤ የኢትዮጵያን ስም እንኳን በአግባቡ ለመጥራት ሲጠየፍ እንደነበርና ኢትዮጵያን መጥቀስ በሚኖርበት ዐረፍተ ነገር ሁሉ “ሀገሪቱ” እያለ በመጥራት ምድራዊውንና የሥልጣን ዘመኑን በአንድ ቅጽበት እስካጣበት ወቅት ድረስ በጥላቻ ናውዞ ይህችን ዓለም የተሰናበተ የመርገምት ፍሬ ነው፡፡ ስለዚህ ጨርቅ ቀርቶ ከዚያም ባለፈ ሊያስከፋ የሚችል ቃል ሊናገር ይችል ነበር፡፡ በንግግር ለማስቀየም ደግሞ እንደመለስ ዘርፋጭ ዓለማችን እስካሁን ያፈራች አትመስለኝም፡፡ እነሂትለርም የዚህን ቆሻሻ ሰውዬ ያህል እንደልባቸው ተናጋሪዎች አይመስሉኝም – መጠነኛም ቢሆን የተወሰኑ የሞራል ዕሤቶችን የሚያከብሩ ይመስሉኛል፡፡ ይሄ የኛው ጉድ  ግን ለይቶለት ከሁሉም ሃይማኖታዊና ሞራላዊ ማዕቀፎች ያፈነገጠ ነበር፡፡

የደብረጽዮን የትግርኛ ንግግርም ከመለስ የሰንደቅ ዓላማን ምንነት አገላለጽ ብዙም ለይቼ አላየውም፡፡ መለስ የኢትዮጵያን መለያ የሦስት ቀለማት ኅብር በሰም ለበስ ቅኔ “ጨርቅ” ሲል ለማዋረድ መሞከሩ ይህም ሰው – ደብረጽዮን – በሚሌኒየም አዳራሽ ለተሰበሰበው፣ ኢትዮጵያንም እንደሚወክል ለሚታመንና በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በሚተላለፍ የቀጥታ ሥርጭት በትግርኛ – ሊያውም ያለ አስተርጓሚ – መናገር የፈለገው  የተለዬ  “ኢንቴንሽን” በወያኔያዊ ልቡ ስላረገዘ እንጂ አንድምታውን አጥቶት አይደለም – የተወሰኑ ምናልባትም ብዙዎቹን የኢትዮጵያን ማኅበረሰብ አባላት በንዴት ለማንጨርጨር የታሰበ ድርጅታዊ ተልእኮን ለማሣካት ፈልጎ መሆን አለበት – በዚህ ጥርጥር የለኝም፡፡ ኦሮሞም በሉት ጉራጌ፣ ደራሳም በሉት ሽናሻ፣ ጠምባሮም በሉት ሃዲያ፣ ከምባታም በሉት ወላይታ፣ ጀምጀምም በሉት ኮንሶ፣ ጉሙዝም በሉት ኣሪ፣ በርታም በሉት አኝዋክ፣ፃማይም በሉት ሱርማ … ሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ – በአዳራሹ ውስጥ ተገኘም በቲቪ ተከታተለም ከትግርኛ ይልቅ በአማርኛ እንደሚግባባ ትግሬ ብቻ ሣይሆን መላው ዓለም ያውቃል፡፡ By the way – በፈረንጅኛው ብራቀቅ ማን ይከለክለኛል –  አሁንም ልድገመውና  By the way የዋሽንግተን ዲሲ አምስተኛው የሥራ ቋንቋ አማርኛ መሆኑን እየመረራቸውም ቢሆን ወያኔዎች ሊያስታውሱት ይገባል – “የሚንቁሽ ዕግርሽ ሥር ወድቀው ይሰግዱልሻል” የተባለችው እምዬ ማርያም ብቻ እንዳልሆነች ልብ ይሏል – ዐማርኛም ገና ምን ዓይታችሁ – ጽላት እስኪቀረጽለት ድረስ በኢትዮጵያ ምድር ከፍ ያለ ሥፍራ ያገኛል – ዐማራ የሚባሉ የወያኔ የዕልቂት ሰለባዎች ከምድረ ገጽ ቢጠፉ እንኳን ዐማርኛ አይጠፋም – በዚህ ላይ ወረድ ብለን ተጨማሪ ነጥቦችን እንመለከታለን፡፡

ይህ ሰው – ደብረጥዮን – በዚህ ድርጊቱ ትግርኛ ተናጋሪውን ማስደሰት ይፈልጋል – ቢያንስ የዋሁን ክፍል፤ ትግርኛ ተናጋሪውን ማስደሰት የሚፈልገው ደግሞ በትግርኛ ፕሮግራም በሚሰራጭ የቴሌቪዥንም ሆነ የሬዲዮ ሥርጭት ሣይሆን ብሔራዊ ሥርጭት የሚካሄድበትን ዋና መስመር በማቋረጥ መሆኑን ያውቃል(ሉ)፤ ጀጋኑ ወዲታት ተጋሩ – ወየንቲ አዲ ትግራይ ኸምዚ’ኢና – ጋና ነርዕዮም ኢና… ይህች ትንሽዬ የዱባ ጥጋብ ከዚህ የምታልፍ መልእክት የላትም – እነዚህን ነፍጠኞች ገና እናሳያቸዋለን እያሉ ይመስላል – እነዚህ ከሙት መንፈስ ጋር ተፋላሚ ዶንኪሾቶች፡፡ በዚህ ሂደት ዐማርኛ ተናጋሪውንና ለጊዜው ማንኛውም ነገር ቢጠበስ ቢገነተር ምንም የማይመስለውን – የማይሞቀውን የማይበርደውን – ከርታታ ዜጋ ብቻ ሣይሆን መላዋን የሀገሪቱን ሕዝብ “ገዢህ እኔ ሕወሓት መሆኔን ሳትወድ በግድህ ዕወቅ፤ ምንም ብታስብ ምን ከኔ በላይ ጌታ ሊኖርህ አትችልም!” የሚል ውስጠ ወይራ መልእክት ለማስተላለፍ የፈለጉ ይመስላል – ቀላል ሰው ከዚህ የሚያልፍ አስተሳሰብ ሊኖረው አይችልምና፡፡ እንጂ ያ በሚሌኒየም ተሰበሰበ የተባለው ሰው ሁሉ ዐማርኛ ቋንቋን አጣርቶ አያውቅም ማለት ማሞ ቂሎን መሆን ነው፡፡ ዐማርኛን እንኳን አዲስ አበቤ ይቅርና እኔም አውቃለሁ ብዬ እንቀባረራለሁ – ከትግራይ ከመጣሁ ከ27 ዓመታት በኋላ፡፡ በአንድ ቋንቋ ውስጥ 50 ዓመትም ኖረህ እኮ ላታውቀውና ላትናገረው ትችላለህ፡፡ የበረከት ስምዖን ወላጆች ጎንደር ውስጥ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ኖረው በዐማርኛ ይቸገሩ እንደነበር በሕይወት ካሉም እንደሚቸገሩ ሰምቻለሁ፡፡

የጀመርኩትን ርዕሰ ጉዳይ በሚመለከት ንግግሩ ሣይሆን ከንግግሩ በስተኋላ ያለው ነገር ነው ለትርጉም ወሳኙ ብዬ ማመን እፈልጋለሁ፡፡ ወያኔ ዐማርኛን አሽቀንጥሮ መጣል ይፈልግ ነበር – ግን አልቻለም – አይችልምም፤ በምን አቅሙ? እየጠላውና እያንገሸገሸውም ቢሆን እስካሁን ለአገዛዙ ተጠቅሞበታል፤ እምትንጠራወዝ እስትንፋሱ ለይቶላት እስክትወጣና ወረደ መቃብር እስኪገባ ድረስም ይጠቀምበታል፡፡ ዐማርኛን ለማጥፋት – ልክ ዐማራ ተብለው የተፈረጁትን ሰዎች ለማጥፋት እንደሞከሩት  – ወያኔዎች ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም – ዐማርኛም ልክ እንደድመት ባለዘጠኝ ነፍስ ሆኖ ግና ክፉኛ ተገዳደራቸው – ሕይወት ያላቸው ተናጋሪዎቹ ሲሸነፉ ግዑዙ ቋንቋ አሸነፋቸውና ሥነ ልቦናዊ የበታችነት ህመማቸውን በየመድረኩ ያዝረከርክባቸውና ለሣቅ ለሥላቅም ይዳርጋቸው ገባ፡፡ ተጋሩ ወንድሞቼንና እህቶቼን የሌሎችን ብሔርና ብሄረሰቦች ስም እየሰጡ፣ ቋንቋቸውንም እንዲማሩ እያደረጉ ብዙ ሥውር ሥራዎችንና ሤራዎችን እንዲሠሩ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡ ነገር ግን እንደዐማርኛ የመሰለ የመግዣ መሣሪያ ሊያገኙ አልቻሉምና እስካሁን ከመድረክ ሊያገልሉት አልተቻላቸውም – ዐፄ ዮሐንስም በዚሁ መሣሪያ ነው አሉ ጎጃምን፣ ወሎንና ጎንደርን አንቀጥቅጥው የገዙት፡፡ በመሆኑም እየጠሉትም ቢሆን፣ ኦሪጂናል ተናጋሪዎችን እያጠፉም ቢሆን፣ ዐማርኛ መናገርን እንደነውር እንዲቆጠር በቀጥታም ሆነ በተዛዋሪ እየሠሩም ቢሆን፣ የቋንቋው ባለቤት እንደሆነ የሚነገርለትን ማኅበረሰብ እየናቁና እያንቋሸሹም ቢሆን፣ በትዕቢትና ዕብሪት ተወጥረው የነሱን ቋንቋና ባህል በሌሎች ላይ ለመጫን እየተንደፋደፉም ቢሆን …  የዐማርኛ ቋንቋን ግን እንደመሣሪያነቱ ሲጠቀሙበት ባጅተዋል፡፡ ምርጫ ስለሌላቸውም ነው፡፡

ቋንቋ የራሱ ህግ አለው፡፡ ማንም እንደፈለገ በዐዋጅ “ይህ ብሔራዊ ይሁን ፤ ያኛው ግን ከዛሬ ጀምሮ ብሔራዊ አይሁን”ማለት አይቻለውም፡፡ እንዲህ ቢቻል ኖሮ የዛሬዋ ዓለማችን የጋራ መግባቢያ ቋንቋ እንግሊዝኛ መሆኑ ቀርቶ የቻይናውያኑ መንደሪን ቋንቋ በሆነ ነበር፡፡ እንደገናም እንዲህ ቢቻል ኖሮ የኢትዮጵያ የጋራም በሉት የሥራ ቋንቋ ኦሮምኛ በሆነ ነበር – እነዚህ ቋንቋዎች በአፍ መፍቻነት እንደሚናገራቸው የሕዝብ ብዛት ቢሆን ኖሮ በየተገለጹበት አድራሻ ኦፊሴላዊ ቋንቋ ከመሆን የሚያግዳቸው አንድም ነገር ባልነበረ፡፡ የሚያግዳቸው ግን የታጠቀ ጉልበተኛ ወያኔን መሰል ውድብ ሣይሆን የማኅበረ-ኢኮኖሚውን መስተጋብራዊ ትስስር ተከትሎ በዘመን ማሕፀን የሚወለደውና የሚያድገው ሥነ ልሣናዊ ነባራዊ ሁኔታ ነው፡፡ እንጂ በቡድኖች ፍላጎት ቢሆንማ ኖሮ የኢትዮጵያ የጋራ ቋንቋ በአሁኑ ወቅት ትግርኛ ከሆነ ቢያንስ 24 ዓመታትን ባስቆጠረ ነበር፡፡ በዶክተር ተብዬዎች የወያኔ አቀንቃኞች የተጻፉ ብዙ ቅዠቶችን አንብቤያለሁ – ለምሣሌ ዐማሮች አናሳ(minority) ጎሣ እንደሆኑ፣ ትግሬው ብዙኃን(majority) እንደሆነ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቋንቋ ትግርኛ እንደሆነ ወዘተ.፡፡

ዐይናችንን እንጨፍንና በተመስጦ ጥቂት እናስብ፡፡ ዐማርኛ ባይኖር ኖሮ አገው ከአደሬው፣ ትግሬው ከቆቱው፣ ከፊቾው ከጉራጌው፣ ኑዌሩ ከሽናሻው፣ ሶማሌው ከኢሣው፣ አፋሩ ከከምባታው፣“ዐማራ”ው ከኦሮሞው፣… በምን ይግባቡ ነበር? ከ80 በላይ ቋንቋዎች በሚነገሩባት ድሃ ሀገር ስንት ብሄራዊ ቋንቋ ማበልጸግ ይቻላል? ከዚህ አኳያ የአፍ መፍቻን ቋንቋን ለአካባቢያዊ አገልግሎት እያዳበሩና እየተገለገሉ ለቅርስነትም እያቆዩ ሁለተኛ ቋንቋን (ተፈጥሯዊ ህግን እስከተከተለ ድረስ ማንኛውም ቢሆን ግዴለኝም) በጋራ ማዳበርና መጠቀም ማንን ይገድላል? በኢትዮዮጵያ ሁኔታና ለኔ እንደሚመስለኝ ይህን የዘመናት የታሪክ ሽመና ያወሳሰበውን ሥነ ልሣናዊ ቁርኝት በ40 ዓመት አይደለም በ400 ዓመትም ቢሆን መበጣጠስ አይቻልም – እርግጥ ነው እዚህና እዚያ በማቆሳሰል የተወሰነ ሰምበርና ጠባሳ ማኖር ይቻል ይሆናል፡፡ አለበለዚያ የኅልውና ጉዳይ ስለሆነ ምድረ ወያኔ ሁላ ጥላቻው እያንዘረዘራትም ቢሆን ዐማርኛዋን እየሰለቀች የአፓርታይድ ሥርዓቷን ትቀጥላለች – የቀብር ሥነ ሥርዓቷ እስኪፈጸም፤ ለነገሩ ዕድር የሌላት ሆና እንጂ ወያኔ እኮ ከሞተች ሰንብታለች – በሕይወት ያለች እየመሰለቻቸው ግን ሰዎች ይፈሯታል – የማይሞት አፏንና የውርድንበር አስደንጋጭ ተግባሯን እያዩ፡፡ ዐማርኛ ቋንቋን በሚመለከት ወያኔ ዕቅዱ ተሣክቶለት ዐማራ የሚላቸውን ወገኖች ከምድረ ገጽ ማጥፋት ቢቻለው እንኳን ዐማርኛን ከጋራ ቋንቋነት አንዲት ጋት እንዲያፈገፍግ ሊያደርገው አይችልም፡፡ ወደሽን ቆማጢት እንዲሉ ነው፡፡ በመሠረቱ ዐማርኛ ብሄራዊ ሆነ አልሆነ ለዐማርኛ ተናጋሪዎች የሚፈይደው ነገር ያለ አይመስለኝም፤ በመንግሥት ደረጃ ከታወጀባቸው የዕልቂት ዐዋጅና ተግባራዊ ማሳደድስ መቼ አስጣላቸው? ቋንቋቸው ብዙኃንን በድልድይነት በማገልገሉ ሳቢያ እንደውለታ ተቆጥሮ ከወያኔ ጭፍጨፋና እንግልት ሊታደጋቸው የሞከረ ማን ነው?

ወያኔዎች እውነተኛ ማንነታቸው ድንገት ብልጭ ሲልባቸው ልክ እንደዛሬው በዐማርኛ ተናጋሪ ኅብረተስበ መካከል – ሳይቸግር ጤፍ ብድር እንዲሉ –  በትግርኛ መቀናጣት ያምራቸዋል – እኔ እንደታዘብኩት ትርፉ ትዝብትና መሣቂያና መሣለቂያ መሆን ነው፡፡ በዚህ ድርጊት ትግርኛ አልከበረም – ዐማርኛም አልተዋረደም፤ የተከበረም ሆነ የተዋረደ ካለ ወያኔ መንደር ውስጥ የሚገኝ ሸውራራና ከፋፋይ አመለካከትና አስተሳሰብ ነው፡፡ በመሠረቱ ቋንቋ እስከዚህ ድረስ ለሥነ ልቦናዊ ቀውስ የሚዳርግ ነገር አይደለም፡፡ ቋንቋ የመግባቢያ መሣሪያ እንጂ የበታችነት ስሜት ጭቅቅትን በሰፊው ሕዝብ ላይ ለማራገፍ የሚዳክሩበት አቢይ ጉዳይ አይደለም፡፡ የማይምነት ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ብዙኃኑ የሚናገረውንና የሚግባባበትን ቋንቋ አስትቶ ወደጠበበ ዐውደ ልሣን የሚያወርድ ምንም ምክንያት የለም፡፡ እርግጥ ነው – በአሁኑ ወቅት ትግርኛ የገዢው መደብ ቋንቋ መሆኑ በስፋት ይታወቃል፡፡ ነገር ግን ለምሣሌ የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ ነገ የዳዋሮ ማኅበረሰብ አባል ወደ ሥልጣን ቢመጣ ዳዋሮኛ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ መግባቢያ ቋንቋ ይሆናል ማለት አይደለም – ሊሆን አይችልም ማለቴ ሣይሆን አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ግን እውነቱ እንደዚያ አለመሆኑን ለመጠቆም ብዬ ነው፡፡ ከፍ ሲል ለመግለጽ እንደተሞከረው ቋንቋ የራሱ ህግና ሥርዓት ያለው እንጂ ገዢዎች እንደፈለጉ የሚዘውሩት እንዳልሆነ መታወቅ ይኖርበታል፡፡ ስለሆነም ደብረጽዮንና በረከት እንዲሁም ሌሎቹ ወያኔዎች እየዳከሩበት የሚገኙት የኢትዮጵያን ሕዝብ የጋራ ቋንቋ የማጥፋትና ወደቀደመው የባቢሎን ዘመን የመመለስ ዕቅድ እንዲህ በቀላሉ ይሣካላቸዋል ብሎ ማመን የዋህነት ይመስለኛል፡፡ እንደኔ እንዲያውም የተቃጠለ አየር ከሰውነቷ እንዳይወጣ ጥረት አድርጋ ነገር ግን ያልተሣካላት ሴትዮ “ውይ! መንግጌ አባስኩሽ!” እንዳለችው እነዚህ ወያኔዎችም ዐማርኛን ለማጥፋት ባደረጉት ጥረት ይበልጥ ተፈላጊነቱን ሣይጨምሩት የቀሩ አይመስለኝም፡፡ እንዴ፣ ቋንቋ እኮ ከእስክርቢቶና ከወረቀት የማይበልጥ ወይም የማያንስ ተራ የመግባቢያ መሣሪያ ነው እንጂ እስከዚህ ድረስ አቅልን ስተው የሚራኮቱበት ነገር አይደለም – በቃ፣ ተራ ነገር ነው፤ ከዚያ አስበልጦ ማየት በሽታን መግዛት ነው – ልክ እንደወያኔ፡፡ ትግርኛ ተናገርክ ዐማርኛ፣ ጦጥኛ ተናገርክ ዝንጀሮኛ፣ አፋርኛ ተናገርክ ኦሮምኛ ዋናው በመግባቢያ መሣሪያነቱ መጠቀም እንጂ “የኔ”ና “ያንተ”ን ምን አመጣው? ያንተ የሆነ የነሱም ነው፤ የነሱ የሆነም ያንተ፡፡ Why should we really over-politicize languages? Personally, I do not see any difference between ‘my’ language and any of the tools I use in my daily life. Aha! I now vividly remember that Esperanto was a failure due to the selfish motive of humans! Hey, let’s get enlightened, please.

የኢትዮጵያ ሕዝብ የቋንቋም ሆነ የዘር ሐረግ ልዩነት እንደማይበግረው በቅርቡ ያዩታል ብዬ አምናለሁ፡፡ ለመሠሪ ተልዕኮና ለአፍራሽ ውጤት ሣይሆን ለእውነተኛው መግባቢያነት ትግርኛም ሆነ ሌላው ቋንቋ ሁሉ በመገናኛ ብዙኃናችን በተፈለገው ጊዜና በተፈለገው መጠን ሲነገር የሚያዳምጡበት ጊዜ ብዙም ሩቅ አይመስለኝም፡፡ ይህችኛዋ የደብርጽዮኒቷ የሚሌኒየም አዳራሽ ትግርኛ ግን “ኢንቴንሽኗ”(ድብቅ አጀንዳ) ትገባናለችና የ“ሲምፕል ሣይኮሎጂ” ሰለባዎች እንዳንሆንላቸው እንጠንቀቅ፤ ወያኔዎችና ሼሪክ አበጋዞቻቸው ሕዝብን ከሕዝብ ለማቃቃር ብቻ ሣይሆን በለዬለት የሁለትና ሦስት ጎራዎች ውጊያ አሠልፈው ለማጨራረስም የማያቅማሙ አረመኔዎችና ኃላፊነት የጎደላቸው ፍጡራን በመሆናቸው ጥንቃቄ ማድረግ ያለብን እኛ ሕዝቡ ነን፡፡ ቀላሎች ቀላል ሊያደርጉን አይገባቸውም፡፡ ሤራቸውን ለማክሸፍ ሕዝቡ በቶሎ መንቃት ይኖርበታል፤ በጥቃቅን መደለያዎች – ሆድን በማይሞሉ የወያኔ የማስመሰል ቅራቅንቦዎች መታለል የለብንም – በሚጨበጥ ነገር እንጂ መሬት ባልረገጠ የስሜት ዐውሎ ነፋስ እንዳንነዳ መጠንቀቅ አለብን፡፡ ከነዚህ አዛኝ ቅቤ አንጓቾች ተንኮል ራሳችንን እንጠብቅ፤ ትግሬውን ያስደሰቱ መስለው ለመታየትና በእግረ መንገድም ስንጥቃቱን ለማስፋት በሚያከናውኗቸው ከፋፋይ ተግባራት ሳንሞኝላቸውና ብዙም ፊት ሳንሰጣቸው በጋራ የጋራ ቤታችን የምትሠራበትን መንገድ እናመቻች፡፡  ትግሬው ወገን የወያኔን ጠባብ ዓላማ ይረዳና ከሰፊው ወገኑ ሊለያየው የሚችልን ይህን መሰል ላይ ላዩን ሲያዩት ምንም ነገር ያልሆነ የሚመስል በጥልቀትና በጥሞና ሲያዩት ግን ሥነ ልቦናዊ መደላድል የረገጠ የከፋፋይነት ሤራ ያለው ተንኮል ተገንዝቦ ተቃውሞውን በግልጽ ማሰማት አለበት፡፡ “የእስካሁኑ መሠሪ አካሄድ ይብቃ” ብሎ እነዚህን የእፉኝት ልጆች ሊታገላቸው ይገባል፡፡ ሌላውም ወገን በዚህ ዓይነት መሠሪ አካሄድ ብዙም ሳይከፋ ለመጨረሻው አርማጌዴዌዎናዊ ድል ይዘጋጅ፡፡ የመጨረሻው መጨረሻ ደወል ሊደወል የቀረው ጊዜ ብዙ ሩቅ አይመስለኝም፡፡ እስከዚያው በያለንበት ሰላም ያቆየን፤ የሀገራችንን ትንሣኤም በቅርብ ያሣየን፤ አሜን፡፡

yiheyisaemro@gmail.com

 

 

The post ከጨርቁና ከቋንቋው በስተጀርባ – ይሄይስ አእምሮ (ከኢትዮጵያ) appeared first on Zehabesha Amharic.

ባለ ራእዩ  መሪ ምን ይሆን ራእያቸው?። (ከ- ከተማዋ ቅጅራ)

$
0
0

ሕልሜን ፍቱልኝ።                                                                                        

KetemaTPLF በአገሩ ሁሉ ለሚኖሩት ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ታላቅ ግብዣ አድርጓል። በዚህ ቤት ሁሌ ደስታ ነው ሁሌ ፌሽታ ነው። ለድግሱ የተጠሩት ሁሉን ማድረግ የሚችሉ፣ ባለብዙ ህንጻ ባሌቤቶች፣ የፈለጉትን የሚወስኑ፣ ራእይ አስፈጻሚ ናቸው። በሚሰሩት ስተት ንጉሱ ከመረጧቸው ከድግሱ ተጠሪዎች ውጪ ማንም ሊጠይቃቸው የማይችል፣ የሚሰሩትን ግፍዊ ስራ  እንደ ጀብዱ  ደጋግመው የሚናገሩ፣ በአዳራሹ ውስጥ ለተሰበሰቡት መገለጫቸው  ነው። በዚህ መሃል ንጉሱ እንዲህ አሉ ለድግሱ ታዳሚዎች በአዳራሽ ውስጥ ላሉት። ህልም አልሜአለው ብለው ተናገሩ። ህልሜም ተፈጻሚነት እንዲኖረው ለድግሱ የተጠራችሁ ወዳጆቼ በሙሉ ሃላፊነት አለባችሁ ከአዳራሹ ውጪ ያልወጣ የንጉሱ ራእይ እንደፈለጉ ሊበሉ ሊጠጡ ለተመረጡት ተነገረ። ወዳጅ ዘመዶቻቸው  የተጠሩት ሁሉ ገብቶአቸው ይሁን ሳይገባቸው በጭብጨባቸው አጸደቁላቸው። ሳይገባቸው ነገሮች እንዲወሰን የሚያደርጉ ሁሉ ታሪክ በኃላ በአጨብጫቢነታቸው እንደሚዘክራቸው ሊያውቁት ይገባል። ህዝቡም የማያውቀው ራእይ ይነገረው ጀመረ። አዲሱ ንጉሳችን  የንግስናው ወንበር በጭንቀት ይሁን በኑዛዜ አልያም በራእይ  ታይቶላቸው ወይም ግራ  ገብቷአቸው ንግስናውን እንዴት  እንደተሰጣቸው ባይገባንም ቅሉ  ብቻ አዲሱ ንጉሳችን  ንግግራቸውን ሲጀምሩ እንዲ አሉ። የቀድሞ ንጉሳችንን ራእይ እናስፈጽማለን። ይሄንን ቃል ደግመው ደጋግመው ይነግሩናል። በመቀጠልም በመቀባበል በተለያዩ ሚዲያዎች እና አጋጣሚዎች የቀድሞ ንጉሳችንን ራእይ እናስፈጽማለን ይሉ ጀመር የአዳራሹ ታዳሚዎች። ራእዩን ያዩትም ሳይነግሩን ሄዱ ራእዩም የተነገራቸው የድግሱ ታዳሚዎችም ስለራእዩ ምንነት ሳይገልጹልን ራእዩን  ለማስፈጸም እሩጫ ሆነ። ለህዝባችን ይፋ ሆኖ ያልተነገረው ራእይ ምን ይሆን?

በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ብዙ ጥያቄዎች ተነሱ ጥያቄዎች በሙሉ በሚያለያይ እና ተቀባይነት በሌለው መልኩ በኃይል ተፈጻሚ ሆኑ። ገዳማዊያን ሳይቀሩ አለም በቃኝ ብለው አፈር ምሰው ጤዛ ልሰው ቅጠል በጥሰው ድንጋይ ተንተርሰው እግዚአብሔር በማመስገን የሚኖሩት ገዳማዊ አባቶች የግፍ በትር አረፈባቸው ታላቅ ተንኮል ተሰርቶባቸው በማያውቁት ነገር ባህታቸው ድረስ ሄደው ገፏቸው ደበደቧቸው። ይሄ ቦታ የናንተ አይደለም  ልቀቁ ተብለው ተዘባበቱባቸው እውን በቤተ ክርስቲያን እና አለም በቃኝ ባሉት አባቶች ላይ የግፍ በትር ማሳረፍ እና ቤተክርስትያንን ማፍረስ ይሆን ራእዩ?

በእስልምና እምነት ላይ ብዙ ሴራ ተሰራ የእምነት መሪያቸውን እንዳይመርጡ የመለያየት ስራ ተደረገ ይመሩናል ያሉትን ትተው ያላሰቡት መሪ ሆኖ በግዳጅ ተጫነባቸው። የለም መሪዎቻችንን እኛ እንምረጥ ባሉት ህዝብ ላይና ጥያቄ ያነሱትን በሙሉ የግፍ በትር ያርፍባቸው ጀመረ። ድምጻችንን ስሙን መሪዎቻችንን እኛው እንምረጥ ያሉትን ህዝብ ላይ ጥያቄውን ከመመለስ ይልቅ የሃይል ዱላ ያሳረፉና  ያሰቃዩ ቀጠሉ።  እስልምናን መከፋፈል  ይሆን እንዴ ራእዩ?

ነጻነት… ነጻነት… ነጻነት… ዲሞክራሲ… ዲሞክራሲ… ዲሞክራሲ…. ፍትህ… ፍትህ…. ፍትህ… ብለው በተናገሩት ነጻ ሰዎች ላይ ቤተሰባቸውን ማሰቃየት ከስራ ገበታቸው ማባረር የመሰብሰቢያ  ቢሮአቸውን በሃይል መዝጋት ስቃይና እንግልት መጫን። ምን አልባትስ   በነጻተት የሚናገር ህዝን እንዳይኖ ስለነጻነቱ የሚቆም ትውልድ እንዳይኖር  ይሆን ራእዩ?

ወንድም ከወንድሙ አጠላልፎ ገንዘብ አምላኪ አድርጎ ትውልዱን መቅረጽ ለምን ተፈለገ?። ስለ ጥቅሙ እንጂ ስለ አገር ክብር ስለ ወገን በደል እንዳያስብ ተደርጎ ያስተምሩታል እንጂ  ወደፊት  አገሩ ከዚህ ትውልድ ብዙ ነገር እንደምትጠብቅ እና ሃላፊነት እንዳለበት  እንዲነገረው ያልተፈለገበት ምን ይሆን ምስጢሩ? የወገን ፍቅር፣ ያገር ፍቅር፣ ከልቡ እንዲወጣ እና እንዳይሳልበት ተደርጎ ትውልድን ማስተማር የድግሱ ታዳሚዎች ምን ይሆን የሚያመጣላቸው ጥቅም? ። አንዱን ሃይማኖት ከሌላው ሃይማኖት ጋር የማጋጨት ስራን መስራት፣  በዘር፣ በጎሳ፣ በብሔር፣ እንዲጠላለፍ ሴራ ማሴር ትርፋቸው ምን ይሆን? ሲሻቸው ማሰር፣ ሲሻቸው ማሰቃየት፣ ሲሻቸው መግደል፣ ባጠቃላይ ህዝብ በሁሉም አቅጣጫ ሲበላላ፣ ሲጠጣላ፣ እና ሲሰቃይ ማየት   ድንገት ይሄ ይሆን እንዴ ራእዩ?

ጥቂቶች ተፈርተው ብዙሃኖቹ ተሸማቀው ማኖር ይሆን ሃሳባቸው። ጥቂቶች ባለስልጣን ሆነው ህዝቡ ለባለስልጣኑ ተገዢ ማድረግ ይሆን እቅዳቸው። ጥቂቶች ሃብታም አድርጎ ብዙኃኑን አደህይቶ የጥቂቶቹን እጅ ጠባቂ ማድረግ ይሆን ፍላጎታቸው። ጥቂቶች ፈላጭ ቆራጭ ህዝብ ግን ተፈላጭ ተቆራጭ እንዲሆን ማድረግ ይሆን ትግላቸው። አገር የቤተሰብ መምሪያ እስከሚመስል ድረስ በአንድ ጎጥ መያዝ ይሆን ራእያቸው?

እንዲህ እንዲህ እያልኩኝ ሃሳቤን የማወርደው ራእዩን ያዩት ባለራእዩ መሪ ራእያቸውን ሳያሳውቁን ስለሄዱ  ነው። ራእዩም የተነገራቸው የድግሱ ታዳሚዎች የአዳራሹ ስብስቦች ምን እንደሆነ ባልነገሩን እና ባላሳወቁን ራእዩን አስፈጻሚ እንደሆኑ  ደጋግመው ይነግሩን  ስለጀመሩ ነው። ታዲያ እየተፈጸሙ ያሉት እነዚህ እና እነዚህን  የመሳሰሉ ናቸው። ንጉሱ ያዩት ራእይ ለህዝቡ ሳይነግሩ ለምን ሄዱ?  ወይስ ጥሩ አማካሪ አልያም ጥሩ ወዳጅ አልነበራቸው ይሆን? ጥሩ አማካሪ አልያም ጥሩ ወዳጅ ቢኖራቸው ያዩትን ራእይ ሊፈቱት የሚችሉ በአገሩ እንዳሉ ይነግሯቸው ነበረ። ያሉት አማካሪ ጥሩ ስላልነበሩ እና የንጉሱን ህልም የሚፈቱትን የእግዚአብሔር መንፈስ ያደረባቸው የሚመጣውንም ያለፈውንም እግዚአብሔር የሚገልጥላቸው እንቆቅልሽን የሚፈቱ  በገዳም የሚኖሩትን መነኮሳት አባቶችን እንኳን አቅርቦአቸው ችግራቸውን ሊያስፈቱ ቀርቶ ገዳማቸው ድረስ ሄደው ማሰቃየትን ነው የመረጡት። ህልም ፈቺዎችን ኢማን ያላቸውን በአላህ መንገድ ያሉ ለአላህ የተገዙ ሼሆችን እያራቁ እና እያሰቃዩ መልካም ነገር መጠበቅ ከባድ ነው። ቅዱሳን አባቶችን ንጉሱ ካጠገባቸው ሊያቀርቧቸው ቀርቶ በገዳማቸው እና በመስኪዳቸው እንዳይኖሩ  ታላቅ በደል እያደረሱባቸው ራእዩ እንዴት ሊፈታ ይቻላል? ማንስ ይፍታው?።

ንጉሱ ያዩትን ራእይ አዳራሽ ውስጥ የተሰበሰቡ የኔ ናቸው ያሉአቸው እንዲበሉ የተፈቀደላቸው በሙሉ ሊፈቱት አይችሉም።  ታዲያ የንጉሱን ራእይ ማን ይፍታው? ግፍ ሲበዛ እግዚአብሔር እራሱ እንዲህ ይፈርዳል።

የእግዚአብሔር እጅ በግፈኖች እና በጨቋኞች ላይ ይወርዳል በእውነትም ፍርዱን እንዲህ ይፈርዳል።

ንጉስ ብልጣሶር ትልቅ ግብዛ አድርጎ ከመኳንቶችን ጋር ከሚስቶቹ ጋር ከእቁባቶቹ ጋር እየጠጣ እና እየጨፈረ ከእንጨት እና ከድንጋይ የተሰሩ አማልክትን ማመስገን ጀመረ። በዚህ ሰአት የሰው እጅ ጣት የንጉሱን አዳራሹን ጥሳ ገባች ግድግዳው ላይ ጽሁፍ ጻፈች። ንጉሱም የሰው ጣት በቤቱ ግድግዳ ላይ ስትጽፍ ተመለከተ። ያን ግዜ  የንጉሱ መልክ  ተለወጠ፣ ልቡ ታወከ፣ የወገቡ ጅማት ተፈታ፣ ጉልበቶቹም ተብረከረኩ።                                                                                                                     ንጉሱም አስማተኖች እና ጠቢባኖች ወደ ንጉሱ ይመጡ ዘንድ አዘዘ። ሁሉም ወደ ንጉሱ ቤት መጡ።ጽፈቱን  ያነቡና ፍችውን ይነግሩት ዘንድ ተናገረ። ይሄን ጽፈት እና ፍቺውን የነገረኝን ሐምራዊ ግምጃ  ይለብሳል በመንግስቴም ላይ ሶስተኛ ገዢ አድርጌ እሾመዋለው ብሎ ተናገረ። በግዛቱ ውስጥ ያሉት አስማተኞች፣ ጠቢባኖች ጽህፈቱን ሊያነቡት አልቻሉም ፍቺውንም ሊያውቁት አልቻሉም። የዚህን ግዜ ንጉሱ ደነገጠ ፊቱም ሲለዋወጥ ባዩት ግዜ መኳንቶቹም ደነገጡ።                                                                               በአገሩ ጥሩ መካሪ አይጥፋ ጥሩም ወዳጅ አያሳጣን ይባላል። ንግስቲቷ የንጉሱንና የመኳንቶቹን ጭንቀት አይታ እንዲህ አለች። አሳብህ  አያስቸግርህ ፊትህም አይለውጥ የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ ያለበት ሰው በመንግስትህ ውስጥ አለ። ማስተዋልና ጥበብ በፊቱ የሆነ እውቀቱ ከእግዚአብሔር የተሰጠው ህልምህን የመተርጎም እንቆቅልሽን የሚገልጥ የታተመውን የሚፈታ ዳንኤል የሚባል ቅዱስ አለና እርሱ ሁሉን ይነግርሃል አለችው። ንጉሱም ተጨንቆ  ስለነበረ በአስቸኳይ ይመጣ ዘንድ አዘዘ።

ዳንኤል ወደ ንጉሱ ቤት ገባ። ንጉሱም የጽህፈቱን ቃል ይፈታለት እና ይተረጉምለት ዘንድ ዳንኤልን ጠየቀው።  ንጉሱ ለዳንኤል ሲናገረው በግዛቴ ያሉትን ጠንቋዮች፣ ጠቢባኖች፣ ፈላስፎች፣ እና ሟርተኖች ጭምር የጽህፈቱት ፍቺ ሊነግሩኝ አልቻሉም። አንተ ግን ሁሉን እንደምታውቅ ተነግሮኛል ጽህፈቱን አንብበህ ከፈታህልኝ ቀይ ግምጃ አልብሼህ በግዛቴ ሶስተኛ ገዢ አድርጌ እሾምሃለው አለው።                                                 ዳንኤልም ያንተን ቀይ ግምጃ እና ሹመት አልፈልግም። ስጦታህም በሙሉ ላንተ ይሁን ነገር ግን ጽህፈቱን አንብቤ ትርጉሙን እነግርሃለው አለው።                                                                                                ጽህፈቱ እንዲህ ይላል ማኔ ቴቄል ፋሬስ የሚል ሲሆን የነገሩም ፍቺ እንዲህ ነው።

ማኔ ማለት እግዚአብሔር መንግስትህን ቆጠራት ፈጸማትም ማለት ሲሆን።

ቴቄል ማለት በሚዛን ተመዘነች ቀላም ተገኘች

ፋሬስ ማለት መንግስትህም ተከፈለች ለመዶንና ለፋርስ ሰዎች ተሰጠች ማለት ነው። ብሎ ቅዱስ ዳንኤል ቃል በቃል ፈታለት። ንጉስ ብልጣሶርም እጅግ ተደሰተ ቀይ ግምጃም አልብሶት በመንግስቱ ላይ ገዚ አድርጎ ሾመው።                                                                                                                        ትንቢተ ዳንኤል ፭(5)+፲፫-፴ (13-30)

ከ- ከተማዋቅጅራ

Email- waqjirak@yahoo.com

The post ባለ ራእዩ  መሪ ምን ይሆን ራእያቸው?። (ከ- ከተማዋ ቅጅራ) appeared first on Zehabesha Amharic.

Hiber Radio: ኢትዮጵያ ከሰሜ ኮሪያ መሳሪያ መግዛት አለመግዛቷን ምርመራ መጀመሩ; እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የ4.9 ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ማቋረጧ; 125 ኢትዮጵያውያን ወደሃገራቸው መላካቸው; የኢትዮጵያን የልብ ትርታ ለማድመጥ ግብፅ የአባይ ወንዝን ለመገደብ ለደቡብ ሱዳን 2 ቢሊዮን ዕርዳታ መመደቧ; ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ለመጠየቅ ቃሊቲ የሔዱ መከልከላቸውና ሌሎችም

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


ህብር ሬዲዮ የካቲት 22 ቀን 2007 ፕሮግራም
እንኳን ለ119ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሰዎ

አቶ ኦባንግ ሜቶ በህብር ሬዲዮ 5ኛ አመት እና 119ኛ የአድዋ ድል በዓል በተከበረበት ወቅት በቬጋስ ተገኝተው ያደረጉት ንግግር(ሙሉውን ያዳምጡ )

<... ...> አቶ ኪዳኔ አለማየሁ የአለም አቀፍ ፍትህ የኢትዮጵያ ጉዳይ ዋና ስራአስኪያጅ ከተናገሩት የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡ )

ስለ ፕሮስቴት ካንሰር ከዶ/ር ሙሉጌታ ካሳሁን ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ
አድዋ ግጥም በመርሻ አያሌው
ጣይቱ ግጥም በሐይማኖት ይመኑ

(ልዩ ዘገባ የሩሲያው የተቃውሞ መሪ መገደልና የቀሰቀሰው አለም አቀፍ ተቃውሞ)
ሌሎችም
ዜናዎቻችን:-
የእንግሊዝ መንግስት ለኢትዮጵያ አገዛዝ የሚያደርገውን የ4.9 ቢሊዮን ዶላር ዕርዳታ ማቋረጡን ገለፀ።

ኢትዮጵያ ማዕቀብ ከተጣለበት ሰሜን ኮሪያ የጦር መሳሪያ ትግዛ ወይም አትግዛ ለማጣራት የተባበሩት መንግስታት ምርመራ ጀመረ

አንድ ከፍተኛ የደቡብ አፍሪካን ዲፕሎማት ከሁለት ዓመት በፊት አዲስ አበባ ላይ ለመግደል በተጠነሰሰ ሴራ እጇ አለበት የተባለችው ሱዳን አቋሟን ገለፀች።

ግብፅ የአባይ ወንዝን ለመገደብ ለደቡብ ሱዳን 2 ቢሊዮን ዕርዳታ መደበች:: የኢትዮጵያን የልብ ትርታ ለማዳመጥ ነው ተብሏል።
የመኢአድ በተለያየ ደረጃ ያሉ ከመጭው የይስሙላ ምርጫ እራሳቸውን ማግለላቸውን ቀጥለዋል ፓርቲው በጉዳዩ ላይ የሰጠው መግለጫ የለም።

125 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከየመንና ከታንዛኒያ ወደአገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ።

የአገር ቤቱ አገዛዝ የፖለቲካ ጥገኝነት የሰጣቸው የቀድሞው የየመን ፕሬዝዳንት ቢሊየነር መሆናቸው ተጋለጠ።

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ለመጠየቅ ቃሊቲ የሔዱ ተከለከሉ። በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞችና ጦማሪያን ዛሬም የአገራቸው የነፃነት ጉዳይ እንደሚያሳስባቸው ገለፁ::

“የነፃነት ጥያቄዎች እስኪመለሱ ሙያዊ ነገሮችን ወደ ጎን ማድረግ ያስፈልጋል:
ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ።
በእስር ላይ የሚገኙት የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ዛሬም የአገራቸው የነፃነት ማጣት እንደሚያሳስባቸው ለጥየቃ ለሄዱ ጋዜጠኞች ገለፁ

The post Hiber Radio: ኢትዮጵያ ከሰሜ ኮሪያ መሳሪያ መግዛት አለመግዛቷን ምርመራ መጀመሩ; እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የ4.9 ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ማቋረጧ; 125 ኢትዮጵያውያን ወደሃገራቸው መላካቸው; የኢትዮጵያን የልብ ትርታ ለማድመጥ ግብፅ የአባይ ወንዝን ለመገደብ ለደቡብ ሱዳን 2 ቢሊዮን ዕርዳታ መመደቧ; ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ለመጠየቅ ቃሊቲ የሔዱ መከልከላቸውና ሌሎችም appeared first on Zehabesha Amharic.

ለአድዋ ድል በቀል ለኢትዮጵያ ስለሚያስፈልገው ፍትሕ -ኪዳኔ ዓለማየሁ

$
0
0

መግቢያ፤

ADWA4-600x310እ.አ.አ. በየካቲት 1896 ባልተጠበቀና እጅግ አስገራሚ በሆነ መንገድ፤ ኢትዮጵያ፤ እስከዚያ ድረስ በየትኛውም ኣሕጉር ተደርጎ የማይታወቀውን፤ አንድ በመልማት ላይ ያለች ሐገር፤ የአንድ ጠንካራ የሆነ የአውሮፓ መንግሥትን፤ የኢጣልያን የጦር ወረራ በድል የተወጣች መሆኑ ለምን ጊዜም ቢሆን በውጭ ጠላት የማትበገር፤ የነጻነት ጮራ ሐገር መሆኗን አረጋግጦላታል። ስለዚህ ታሪካዊ አኩሪ ድል፤ ብዙ ተጽፏል፤ የአድዋ ክብረ-በዓል በሚዘከርበት ጊዜም፤ ዝርዝር ታሪኩና አንድምታው በሰፊው ይነገራል፤ ይጻፋል። የዚህ ጽሑፍ ትኩረት ግን፤ በመጀመሪያ፤ የአድዋው ጦርነት ዋናው መንሰኤ ኢጣልያ ኢትዮጵያን የቅኝ ግዛቷ ለማድረግ የነበራት አጉል ምኞት ቢሆንም፤ የቀሰቀሰው አንደኛው ምክንያት የትርጉም ጠንቅ የነበረበት የውጫሌው ውል ስለ ነበር፤ ውሉ በአጼ ምኒልክና በኢጣልያኑ ተወካይ በአንቶኒሊ እንደ ተፈረመ፤ ወዲያውኑ በራስ መኮንን የተመራ አንድ የልዑካን ቡድን ወደ ኢጣልያ ተጉዞ ስለ ፈጸመው ጠቃሚ የዲፕሎማሲ ተግባር፤ ሁለተኛም አድዋ ላይ ለተከናነበችው እጅግ አሳፋሪ ሽንፈት፤ ኢጣልያ 40 ዓመት ሙሉ ጠብቃና ተዘጋጅታ፤ በቫቲካን ያልተቆጠበ ድጋፍ፤ በኢትዮጵያ ላይ ስለ ፈጸመችው አሰቃቂ የበቀል የጦር ወንጀል፤ ዳግመኛ ድል ብትነሳም፤ ለኢትዮጵያ ተገቢ የሆነ ፍትሕ ስለ አለመገኘቱና በመኪያሔድ ላይ ስላለው ትግል አጭር ዘገባ ይቀርባል።

[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

The post ለአድዋ ድል በቀል ለኢትዮጵያ ስለሚያስፈልገው ፍትሕ -ኪዳኔ ዓለማየሁ appeared first on Zehabesha Amharic.

አበበ ገላው የዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖምን የ20 ሚሊዮን ዶላር ቅጥፈት አጋለጠ

$
0
0

dr_tedros_adhanom
ቴድሮስ አድሃኖም ያራገቡት የ20 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት የፈጠራ ወሬ መሆኑ ተረጋገጠ * የአውስትራሊያ መንግስት እና የሮተሪ ፋውንዴሽን በሪቱ ጃለታን አናውቃትም ገንዘብም አልሰጠንም አሉ

በአበበ ገላው

(አዲስ ቮይስ) ሰሞኑን የህወሃት መራሹ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሆኑት ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በአንድ የአውስትራሊያ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ውድድር አሸናፊ በመሆን እና አስደናቂ ውጤት በማምስመዝገብ 20 ሚሊዮን የአውስትራሊያ ዶላር በማሸነፍ ያገኘችውን ገንዘብ ለልማት ለማዋል ኢትዮጵያ ትገኛለች የተባለችን የ14 አመት ልጅ በመገናኛ ብዙሃን እና በማህበራዊ ድረ ገጾች ከማስተዋወቅ አልፈው በቢሯቸው ከልጅቷ ጋር ጋዜጣዊ መግለጫ መስጠታቸው ይታወሳል።

ሚኒስትሩ በሪቱ ጃለታ አህመድ ገና በለጋ እድሜዋ ይህን ያህል ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለልማት በማዋሏ ለኢትዮጵያዊያን በተለይ ደግሞ ለዲያስፖራው አርአያ መሆኗን በይፋ አውጀው ነበር። ወጣቷ የሽልማት ገንዘቡን በሙሉ አባቷ አቶ ጃለታ አህመድ በተወለዱበት በምስራቅ ሀረርጌ፣ ጋራ ሙለታ፣ ትምህርት ቤት ልታሰራበት ማቀዷን ለጋዜጠኞች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተገኝታ ከሚኒስትሩ ጋር በጋራ በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ይፋ ያደረገች ሲሆን ገንዘቡ የተገኘው ከፊሉ ከአውስትራሊያ መንግስት፣ ከፊሉ ደግሞ ከአውስትራሊያ የሮተሪ ክለብ መሆኑን ይፋ አድርጋ ነበር።
tewedros
ይሁንና ሸልማቱን አዘጋጀ የተባለው ባደን ፓወል ኮሌጅ በመባል የሚጠራው የመንግስት ትምህርት ቤት ስለጉዳዩ ምንም የሚያውቀው ነገር ባለመኖሩ ግራ በመጋባት ጉዳዩን ለምርመራ ወደ ፖሊስ መምራቱን ለማረጋገጥ የቻልን ሲሆን የአውስታራሊያ መንግስት እና ሮታሪ ፋውንዴሽን በበኩላቸው ለአዲስ ቮይስ በተናጠል በሰጡት መግለጫ እንዳረጋገጡት ለታዳጊዋ ምንም አይነት ገንዘብ አለመስጠታቸውን እንዲሁም ስለ እርሷም ሆነ ስለተባለው ውድድርና ሽልማት ሰምተው እንደማያውቁ አረጋግጠዋል።

የአውስትራሊያ የውጭ ጉዳይና ንግድ ሚኒስቴር በጹሁፍ በላከልን መግለጫ አንደገለጸው የአውስትራሊያ መንግስት በኢትዮጵያ ጋራ ሙለታ ትምህርት ቤት ለማሰራት 10 ሚሊዮን ዶላር ሰጠ መባሉን አስተባብሏል። ሚኒስቴሩ አክሎም በኢትዮጵያ ለትምርት በቀጥታ ድጋፍ ባይሰጥም ኢትዮጵያ ከሌሎች ሃገሮች ጋር ተጠቃሚ በሆነችበት አለም አቀፍ የትምህርት የጋራ ትብብር (Global Education Partnership) በኩል ድጋፍ እንደሚሰጥ ጠቁሞ ኢትዮጵያ በትብብሩ በኩል በሚሰጠው የገንዘብ እርዳታ ተጠቃሚ ነች በማለት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ጄና ሃንድ አክለው ገልጸዋል።
Bruce Allen
በአውስትራሊያ የሮታሪ ፋውንዴሽን ስራ አስኪያጅ የሆኑት ብሩስ አለን በበኩላቸው ስለ ተሸላሚዋም ልጅም ይሁን ስለሽልማቱ ከዚህ በፊት ሰምተው እንደማያውቁ አስገንዝበው ድርጅቱ የተባለውን ያህል መጠን ያለው ገንዘብ እንኳን ለልጅ ሊሰጥ ለራሱም የበጎ አድራጎት ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ በቂ ገንዘብ እንደሌለው አስረግጠው ተናግረዋል። ስራ አስኪያጁ አክለው እንደገለጹትም ባለፈው አመት የበጀት አመት ሮተሪ በ አውስትራሊያ ያሰባሰበው ገንዘብ መጠን 5.6 ብቻ መ ሆኑን ጠቁመው 10 ሚሊዮን ዶላር ለልጅቷ በሽልማት መልክ ሰጠ መባሉ በጣም የሚያሳዝን ክስተት መሆኑን ገልጸዋል። ባለፈው አመት ሮታሪ ኢንተርናሽናል በአለም አቀፍ ለትምህርት ነክ እንቅስቃሰዎች የሰጠው ገንዘብ 6.5 ሚሊዮን ዶላር በቻ የበረ ሲሆን ይህም ገንዘንብ ለ66 ፕሮጄክቶች መከፋፈሉን ለማወቅ ተችሏል።

ከዚህ በፊት በአለም ላይ ተሰምቶና ታይቶ የማይታወቀውን ይህን “ታልቅ ውድድር” እና የ20 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት አዘጋጀ የተባለው የአውስትራሊያው የመንግስት ትምህርት ቤት1800 ተማሪዮችና 180 ሰራተኞች የሚሆኑ ያለከፍያ በበጎ አቃድ የሚሰሩ ሰራተኞች ያሉት ሲሆን አመታዊ በጀቱ 12 ሚልዮን የአውስትራሊያ ዶላር ነው። ይህም ማለት የትምህርት ቤቱ አመታዊ በጀት ለ14 አመቷ ልጅ ሰጠ ከተባለው ሽልማት በ8 ሚሊዮን ዶላር የሚያንስ ሲሆን የሽልማት ገንዘቡን ትምህርት ቤቱ እንዴት እንዳሟላው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩም ይሁኑ ተሸላሚዋ በጋዜጣዊ መግለጫቸው ላይ ማብራሪያ አልሰጡም።

ሌላው አስገራሚ ጉዳይ በሪቱ ሽልማቱን አገኝ በተባለው ያለፈው የበጀት አመት የአውስትራሊያ መንግስት በገዘብ እጦት ምክንያት ከሰሃራ በታች ላሉ የአፍሪካ አገሮች የሚሰጠውን እርዳታ መጠን ከ225 ሚሊዮን በ37በመቶ በመቀነስ ወደ 133 ሚሊዮን የአውስትራሊያ ዶላር በመቀነሱ በአለም አቀፍ ደረጃ ሲተች የበነረ ሲሆን የበጀት ቅነሳ ያደረገው ለልጅቷ ለመስጠት አለመሆኑን ግን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ መግለጫ ለመረዳት ተችሏል።
ይሁንና ይህ ጉዳይ በዙዎች ዘንድ ሆን ተብሎ ለስውር አልማ የዋለ የህወሃት ውስብስብ ተንኮል ጋር የተያያዘ ነው በማለት ጥራጣሪያቸውን በስፋት በመግለጽ ላይ ይገኛል ።

The post አበበ ገላው የዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖምን የ20 ሚሊዮን ዶላር ቅጥፈት አጋለጠ appeared first on Zehabesha Amharic.

ወሬ ሲነግሩህ ሃሳብ ጨምርበት –(በእውቀቱ ስዩም)

$
0
0

Bewketu Seyoum – Hagere Mariam (Maryland) USA [Must Listen)

ምኒልክ ጥቁረቱን ክዶ ነበር የሚል ቀደዳ በፌስቡክ ሲዞር ኣየሁ ልበል?
ትልልቅ ቅጥፈቶች ጀርባ ኣንድ ትንሽ መነሻ ይኖራል፡፡
መነሻውን እንመርምር እስቲ፡፡

ያድዋ ድል ማግስት የምኒልክ ዝና የጠራቸው የውጭ ኣገር ሰዎች ኢትዮጵያን መጎብኘት ጀምረው ነበር፡፡ ከኒህ እንግዶች ኣንዱ የሄቲው ታጋይ ጋዜጠኛ ቤኒቶ ሲልቪያን ነው፡፡
ሲልቪያንና ምኒልክ ያደረጉትን ጭውውት ስኪነር የተባለ ኣሜሪካዊ ዘግቦታል፡፡
በጭውውታቸው መሀል ምኒልክ ለሄቲው ሰውየi am not a Negro I am a Caucasian ማለቱን ስኪነር ዘግቧል፡፡

ምኒልክ ኔግሮ ኣይደለሁም ብለው ከሆነ ደግ ኣደረጉ ከማለት ውጭ የምለው የለኝም፡፡ ምኒልክ ጥቁር እንጂ ኔግሮ ኣይደለም።ኔግሮ የውርደት ስም ሲሆን ጥቁር የክብር ስም ነው፡፡
ኮኬሽያን የሚለው ቃል ግን ያስተርጓሚ ስተት መሆን ኣለበት፡፡በምኒልክ ዘመን ሰዎች ዘርን ለመግለጽ የሚጠቀሙባቸው ቃላት ከብሉይና ሃዲስ የተቀዱ ናቸው፡፡የሴም ዘር የካም ዘር የያፌት ዘር ወዘተ ይሰኛሉ፡፡ ኮኬሽያን የሚለው ቃል በወዘተ ውስጥ ኣይካተትም፡፡ኮኬሽያን በጊዜው በሊቃውንቱም ሆነ በመኳንንቱ ኣንደበት የሚዘወተር ቃል ኣልነበረም፡፡

ምኒልክ የሚገዛቸው ህዝቦች ጥቁር እንደሆኑ ያምን ነበር፡፡
እንደ ኤውሮፓ ኣቆጣጠር በ1878 ለንጉስ ሊዎፖልድ በጻፈው ደብዳቤ እንዲህ ይላል፡፡
“የኦሮሞ (ቃሉ ተተክቷል) የኣማራ የሱማል መልኩ ኣንድ ነው፡፡ ሁሉም ጥቁር ነው፡፡”

ምንጭ Acta Ethiopia vol 3 Edited by Sven Rubenson page302

ምኒልክ ጥቁረቱን ከመቀበል ኣልፎ ኣፍሪካዊ ጌቶች ጋር ጥቁረትን መሰረት ያደረገ ትብብር ጠይቆ ያውቃል፡፡ለምሳሌ ከሱዳኑ የማህዲስት መሪ ጋራ ሲደራደር የተናገረውን ታሪክ ጸሃፊዎች እንዲህ መዝግበውታል፡፡
Between us there has been no war. Now we have worse enemy who will make slaves of you and me.I am black :and you are black. Unite with me”
ትርጉም፤

”ባንተናኔ መሀል ጠብ ኖሮ ኣያውቅም፡፡ሁለታችንን በባርነት ሊገዛን የተሰናዳ የከፋ ጠላት ኣለብን፡፡ እኔ ጥቁር ነኝ፡፡ ኣንተም ጥቁር ነህ፡፡ እንተባበር“
ልብ በሉ ይህንን የሚለው ምኒልክ ነው፡፡
በካሊፋውና በምኒልክ መካከል የተደረገው ይህ ታሪካዊ ልውውጥ ተመዝግቦ የተገኘው ከጥልያኑ መኮንን ከባራቴሪ ማስታወሻ ውስጥ ሲሆን በእንግሊዝኛ ተርጉማ መጽሃፏ ውስጥ የዶለችውChris Prouty ናት፡፡Empress Taitu and Menilk በተባለው መጽሀፏ ገጽ 119 ላይ ታገኙታላችሁ፡፡
በተረፈ “ወሬ ሲነግሩህ ሀሳብ ጨምርበት”የሚለውን ያባቶቻችንን ምክር በመጋበዝ ልሰናበት፡፡

The post ወሬ ሲነግሩህ ሃሳብ ጨምርበት – (በእውቀቱ ስዩም) appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: ንዴት የሚያስከትላቸውን 4 የጤና ችግሮች ይወቁ

$
0
0

Anger 2
(በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር)

1. ለድንገተኛ የልብ ሕመም ያጋልጣል
በቶሎ የሚበሳጩ እና የሚናደዱ ከሆነ ራስዎን ለድንገተኛ የልብ ሕመም እያጋለጡ እንደሆነ ሊያውቁ ይገባል፡፡
2. አሉታዊ ስሜታዊነት ሰውነትዎን ለሕመም ያጋልጣሉ
ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ ከ85% በላይ የሚሆኑ የበሽታ ዓይነቶች ከሚኖረን ስሜት ጋር ተያያዥነት አላቸው፡፡
3. ንዴት በውስጥዎ ማመቅ ለድንገተኛ የልብ ሕመም ተጋላጭነትዎን በ3 ዕጥፍ ይጨምራል
በሚናደዱ ጊዜ ንዴትዎን ለማብረድና መፍትሔ ለመፈለግ ራስዎን የሚዝናና እና ንዴትዎን ሊቀንስ ሰለሚችል ነገርን ያድርጉ፡፡ ይህን የማያደርጉ ከሆነ እራስዎን ለልብ ሕመም በከፍተኛ ሁኔታ ያጋልጣሉ፡፡
4. የሰውነትዎን በሽታ የመከላከል አቅም ይቀንሳል
ንዴት በሰውነትዎ ውስጥ የሚገኙ በሽታ ተከላካይ የሆኑ ሴሎች እንዲዳከሙ እና በቀላሉ በበሽታ እንዲጠቁ መንገድ ይክፍታል፡፡
ንዴት ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮች እና ሌሎችንም ስለሚያስከትል ቢቻል ባይናደዱ አልያም በዕለት ተዕለት የኑሮ ሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ እክሎችን በተረጋጋ መንፈስና ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲፈቱና ጤንነትዎን አደጋ ላይ እንዳይጥሉ ስል አመክራለሁ፡፡
ጤና ይስጥልኝ

The post Health: ንዴት የሚያስከትላቸውን 4 የጤና ችግሮች ይወቁ appeared first on Zehabesha Amharic.


የጥርስ መቦርቦር

$
0
0

Thooth Deay
(በዶክተር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር)
የጥርስ መቦርቦር የሚከሰተው በአፋችን ውስጥ የሚገኙ ጀርሞች (ባክቴሪያ) ጥርሳችንን የሚያበሰብሱ አሲዶችን በሚያመነጩበት ጊዜ ነው፣ ይህም በጥርሳችን ላይ የተቦረቦሩ ቀዳዳዎችን (Cavities) እንዲፈጠሩ ያደርጋል። የተቦረቦሩ ጥርሶች ህመም ከማስከተል ባለፈ ለኢንፌክሽን ያጋልጣሉ።
✔ የጥርስ መቦርቦር እንዴት ይከሰታል?
– በጥርስ ላይ ተለጥፈው የሚቀሩ ምግቦች ካልተፀዱ ይከማቹና የባክቴሪያዎች መራቢያ እና ምግብ ይሆናሉ። ባክቴሪያዎች በሚመገቡ ጊዜ ከውስጣቸው አሲድን ይረጫሉ፣ ይህም ጥርሳችን እንዲቦረቦርና እንዲበሰብስ ያደርጋል።
✔ ለጥርስ መቦርቦር የሚያጋልጡ ሁኔታዎች
– ጥርስን በሚገባና በመደበኛ ሁኔታ አለማፅዳት
– ጣፋጭነት የበዛባቸው ምግቦች ማዘውተር
– የፍሎራይድ እጥረት መኖር
– የስኳር ህመም ተጠቂ መሆን
– በህመም ወይንም በተለያዩ መድሀኒቶች ምክንያት የአፍ ድርቀት ሲኖር
– ሲጋራን ማጤስ ናቸው።
✔ የጥርስ መቦርቦር የሚያስከትላቸው ምልክቶች
– የጥርስ ህመም ስሜት
– በተጎዳው ጥርስ አካባቢ የድድ ማበጥ
– መጥፎ የሆነ የአፍ ጠረን መኖር
– በጥርስ ላይ ነጭ፣ ግራጫ፣ ቡኒ ወይንም ጥቁር ቀለማት የያዙ የተቦረቦሩ ቦታዎች መኖር ናቸው።
✔ የጥርስ መቦርቦርን እንዴት መከላከል ይቻላል?
* ጥርስዎን በቀን ውስጥ ቢያንስ ሁለት ጊዜ (ከቁርስ በኃላ እና ከመተኛትዎ በፊት) የፍሎራይድ ኬሚካል ባለው የጥርስ ሳሙና መታጠብ።
* በማንኛው ግዜ ምግብ ከተመገቡ በኃላ አፍዎን በንፁህ ውሀ በሚገባ መጉመጥመጥ
* ከእንቅልፍ በፊት ጥርስዎን ከታጠቡ በኃላ ምንም አይነት ምግብ አለመመገብ
* ጣፋጭ የበዛባቸው ምግቦችን ከምግብ ፕሮግራም ውስጥ ማስወገድ
* ልጆች ለጥርስ መቦርቦር ተጋላጭነታቸው ከፍተኛ ስለሆነ ሁሌም ስለ ጥርስ ፅዳት አጠባበቅ ማስተማር
* የጥርስ ሀኪምዎ ጋር በዓመት አንድ ጊዜ በመሄድ ጥርስዎን በባለሞያ ማሳጠብና ማስመርመር
ማሳስቢያ:
————
የጥርስ ህመም ሲሰማዎ ጊዜ ሳይሰጡ ወደ ሀኪም መሄድን አይዘንጉ ምክንያቱም የህመም ስሜቱ ከጥቂት ጊዜ በኃላ በራሱ ሊጠፋ ቢችልም የጥርስ መቦርቦር ግን ያለ ህመም ሊቀጥል ይችላል። በአፋጣኝ ህክምና ካልተደረገ ጥርስዎን እስከማጣት ሊያደርስዎ ይችላል።
ለወዳጅዎ ያካፍሉ
ጤና ይስጥልኝ

The post የጥርስ መቦርቦር appeared first on Zehabesha Amharic.

ሰማያዊ ፓርቲ ይፋዊ የምርጫ ቅስቀሳ ቢጀምርም ለቅስቀሳ የወጡት እየታፈኑ መሆኑ ተገለጸ

$
0
0

semayawi party
ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ የካቲት 24/2007 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሁሉም ክፍለ ከተሞች ይፋዊ የምርጫ ቅስቀሳ መጀመሩን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ይፋዊ የምርጫ ቅስቀሳ ጀመረ:የምርጫ ቅስቀሳ ቡድን ፖሊስ ጣቢያ ተወሰደ፡፡

በዛሬው ዕለት ፓርቲው የመኪና ላይ የድምጽ ቅስቀሳ እያደረገ ሲሆን ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች በራሪ ወረቀቶችንም እያደለ ይገኛል፡፡

ይህ በ እንዲህ እንዳለ በሽሮሜዳ አካባቢ በቅስቀሳ ላይ የሚገኘው የምርጫ ቅስቀሳ ቡድን በፖሊስ ታግቶ ወደ ፖሊስ ጣቢያ እየተወሰደ ነው፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በዛሬው ዕለት ፓርቲው የመኪና ላይ የድምጽ ቅስቀሳ እያደረገ ሲሆን ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች በራሪ ወረቀቶችንም እያደለ ይገኛል፡፡ በሽሮሜዳ አካባቢ በቅስቀሳ ላይ የሚገኘው የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ቡድን በአሁኑ ሰዓት በፖሊስ ታግቶ ወደ ፖሊስ ጣቢያ እየተወሰደ ነው፡፡ ፖሊስ ከበላይ የመጣ ትዕዛዝ ነው ከማለት ያለፈ ለአፈናው ምንም ምክንያት አልሰጠም::

በሌላ ዜና የምርጫ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ ሁለት የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎች ታሰሩ::
ዛሬ የካቲት 24/2007 ዓ.ም በአዲስ አበባ ጉለሌ ክፍለ ከተማ የምርጫ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ ሁለት የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎች በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል፡፡ ፓርቲው ዛሬ በሁሉም የአዲስ አበባ ክፍለ ከተሞች ላይ በጀመረው ቅስቀሳ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ቅስቀሳ ላይ የነበሩት ዘላለም ደሳለኝ፣ ምዕራፍ ይመር፣ ይድነቃቸው ፍሬው ተክለና ሳምሶን ግዛቸው ሽሮ ሜዳ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው ከቆዩ በኋላ ወደ ላዛሪስት ፖሊስ ጣቢያ ተዛውረዋል፡፡ ከታሰሩት አራት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መካከል ዘላለም ደሳለኝና ይድነቃቸው ፍሬው ዕጩ ተመራጮች ናቸው፡፡
ፖሊሶች በቅስቀሳ ላይ የነበሩትን አባላት በያዙበት ወቅት ‹‹ተልከን ነው›› ማለታቸው የታወቀ ሲሆን ‹‹ቅስቀሳ በቴሊቪዥን እንጅ በመኪና አልተፈቀደም፣ ቅስቀሳ መፈቀዱን አናውቅም፣ ይቀስቅሱ የሚል መመሪያ አልተላለፈልንም›› የሚሉ ምክንያቶችን መስጠታቸው ታውቋል፡፡

The post ሰማያዊ ፓርቲ ይፋዊ የምርጫ ቅስቀሳ ቢጀምርም ለቅስቀሳ የወጡት እየታፈኑ መሆኑ ተገለጸ appeared first on Zehabesha Amharic.

በዝቋላ ገዳም ዙሪያ የእሳት ቃጠሎ ተቀሰቀሰ * የእሳት ቃጠሎው የጀመረው ወንበር ማርያም እየተባለ በሚጠራው በገዳሙ ሰሜናዊ አቅጣጫ ነው

$
0
0

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊበን ዝቋላ ወረዳ አዱላላ ከተማ በሚገኘው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ዙሪያ የእሳት ቃጠሎ መቀስቀሱን የገዳሙ መነኰሳት እየተናገሩ ነው፡፡

ከጠዋቱ 2፡00 ገደማ የተቀሰቀሰው የእሳት ቃጠሎው የጀመረው ወንበር ማርያም እየተባለ በሚጠራው በገዳሙ ሰሜናዊ አቅጣጫ ነው፡፡

ይህ አቅጣጫ፣ የገዳሙ ሞፈር ቤት የሚገኝበት መውጫ መንገድ ሲኾን በአኹኑ ሰዓት በበርካታ ቦታዎች ጭስ እንደሚታይ በመነኰሳቱ ተገልጧል፡፡

የቃጠሎው መንሥኤ በውል ባይታወቅም እሳቱ በአካባቢው ባለው ከባድ የነፋስ ኃይል ወደ ገዳሙ መውጫና በገዳሙ ዙሪያ እንዳይስፋፋ ተሰግቷል፡፡

የአቅራቢያው ነዋሪ ኅብረተሰብ በጥሩንባ በተላለፈው የድረሱልን ጥሪ የተሰባሰበ ሲኾን ወደ ወረዳው ጽ/ቤትም ተደውሎ የአስተዳደሩ አባሎችና የፖሊስ ኃይል በስፍራው መድረሳቸው ተገልጧል፡፡ ‹‹ቃጠሎውን በቅጠልና በአፈር ለመከላከልና መዛመቱን ለመቀነስ የነፋሱን ጋብ ማለት እየተጠባበቅን ነው ብለዋል፤›› አንድ የገዳሙ መነኰስ፡፡

በጥንታዊውና ታሪካዊው ገዳም ዙሪያ የእሳት ቃጠሎ ሲደርስ የአኹኑ የመጀመሪያ አይደለም፡፡ መጋቢት ፲ ቀን ፳፻፩ ዓ.ም. በደረሰው የእሳት ቃጠሎ እንደ አርዘ ሊባኖስና የሐበሻ ጥድ ያሉት አገር በቀል ዛፎች በስፋት ወድመዋል፡፡ መጋቢት ፰ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም. የተቀሰቀሰው ቃጠሎ ደግሞ ተኣምራዊና ግራ አጋቢ ጠባይዕ የታየበት ነበር፡፡ በምሥራቃዊ አቅጣጫ በሚገኘው የመንግሥት ደን ውስጥ ተከሥቶ በአንድ ገጽ ኃይሉ ሲቀንስ በሌላ አቅጣጫ እየተዛመተ ገዳሙን ጨርሶ ለማጥፋት በተቃረበበት ኹኔታ ከአዲስ አበባ፣ ከቢሾፍቱና ከአዳማ በተመሙ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ በጎ አድራጊ ምእመናንና አካላት መተባበር እንዲኹም በመከላከያና በፖሊስ ኃይሎች እገዛ መገታቱ የሚታወስ ነው፡፡
gedam
በመጪው መጋቢት ወር መጨረሻ በገዳሙ የጠበል – ሐይቅ የኢሬቻን በዓል ለማክበርና በደብረ ዝቋላ የአባ ገዳ ሐውልት ለመትከል በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የባህልና ቱሪዝም ቢሮ መታቀዱንና በመንግሥት ብዙኃን መገናኛ መገለጹን ተከትሎ ቤተ ክርስቲያናችን በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በኩል ለክልሉ ርእሰ መስተዳድር በጻፈችው ደብዳቤ ተቃውሞዋን በማሰማት ላይ እንዳለች ይታወቃል፡፡ጥንታዊውና ታሪካዊው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ዛሬ በሚታወቅበት ቦታ ላይ ከተገደመ ከ700 ዓመታት በላይ አስቆጥሯል፡፡ በገዳሙ ደጅ ጠኚውን፣ አፈር ጠባቂውንና የአብነት ትምህርት መምህራንና ደቀ መዛሙርትን ሳይጨምር እስከ 350 መነኰሳትና መነኰሳዪያት እንደሚገኙበት ተዘግቧል፡፡

The post በዝቋላ ገዳም ዙሪያ የእሳት ቃጠሎ ተቀሰቀሰ * የእሳት ቃጠሎው የጀመረው ወንበር ማርያም እየተባለ በሚጠራው በገዳሙ ሰሜናዊ አቅጣጫ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

የአማራ ክልል ከተሞች ልማትና ግንባታ የሰማያዊ ፓርቲ አመራርን ከኃላፊነቱ አነሳ

$
0
0

‹ውሳኔው ፖለቲካዊ ነው›› አቶ አዲሱ ጌታነህ

11043128_885271564848776_4028315024485403437_nየአማራ ክልል ከተሞች ልማትና ግንባታ የሰማያዊ ፓርቲ የምዕራብ ጎጃም ዞን ተወካይ እንዲሁም የምዕራብ ጎጃም፣ ምስራቅ ጎጃምና አዊ ዞን የምርጫ ግብረ ኃይል አባል የሆነውን አቶ አዲሱ ጌታነህን ‹‹ማኔጅመንቱን ያውካል፣ የስራ ተነሳሽነት የለውም›› በሚል ከኃላፊነቱ ማንሳቱን በደብዳቤ አሳውቋል፡፡

ይሁንና መስሪያ ቤት ጥቅምት 23/2007 ዓ.ም በብቃቱ መሰረት በኃላፊነት እንደመደበው በደብዳቤ የገለጸ ሲሆን አሁን የተወሰደው እርምጃ ከወቅቱ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ጋር የተያያዘ መሆኑን አቶ አዲሱ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

‹‹ባህርዳር ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ኃይል እየተፈጠረ ነው፡፡ በተለይ የአንድነት መዋቅር ሰማያዊን ከተቀላቀለ በኋላ ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ይህንም ተከትሎ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች ጋር ያደረግናቸው ውይይቶች ብአዴንን አስደንግጦታል›› ያለው አቶ አዲሱ መስሪያ ቤቱ የወሰደበት እርምጃ ፖለቲካዊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የምዕራብ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ መዋቅር በአካባቢው ህዝብ ላይ የሚደርሰውን በደል፣ እንዲሁም ምርጫ ቦርድ ከዕጩ ምዝገባ ጋር በተያያዘ የሚፈጥራቸውን ችግሮች ለሚዲያ በማጋለጥ ላይ መሆኑ ከኃላፊነት ለመነሳቴ አንድ ምክንያት ነው ሲል ገልጾአል፡፡

የአማራ ክልል ከተሞች ልማትና ግንባታ የቦርድ አባላት የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች ሲሆኑ ከእነዚህም መካከል የባህርዳር ከተማ ከንቲባ አቶ ላቀ አያሌው፣ የክልሉ ም/ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ያለው አባተ፣ የክልሉ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ኃላፊ አቶ አየነው ይገኙበታል፡፡

The post የአማራ ክልል ከተሞች ልማትና ግንባታ የሰማያዊ ፓርቲ አመራርን ከኃላፊነቱ አነሳ appeared first on Zehabesha Amharic.

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ 25ኛ ዓመት በዓለ ሢመትና በዋሽንግተን ዲሲ

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live