Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

አስተዳደሩ የትብብሩን የ24 ሰዓት ሰላማዊ ሰልፍ እውቅና አልሰጠሁም አለ

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ

negere-ethiopia-photo1•ትብብሩ አስተዳደሩ እውቅና ሰጭም ነፋጊም አለመሆኑን በመግለጽ ድጋሜ ደብዳቤ ጽፏል
የ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 27 እና 28/2007 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ሊያደርገው ላቀደው የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግለት፣ ህዳር 17 ቀን 2007 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ መጠየቁ የሚታወስ ቢሆንም አስተዳደሩ በቁጥር አ.አ/ከፅ/10/30.4/55 ህዳር 19 ቀን 2007 ዓ.ም በፃፈው የመልስ ደብዳቤ ለሰላማዊ ሰልፉ እውቅና አለመስጠቱን አስታውቋል፡፡

ትብብሩ ለሰልፉ የመረጠው ቦታ መስቀል አደባባይ ሲሆን፣ አስተዳደሩ በበኩሉ የ24 ሰዓቱን ሰልፍ ላለማወቁ ምክንያት ነው ያለውን ሲያስቀምጥ፣ ‹‹የተጠየቀው ቦታ በልማት ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅና ትላልቅ የመንግስት ተቋማት እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ያሉበት ስለሆን ጥያቄውን ተቀብለን ለማስተናገድ የምንቸገር መሆኑን እየገለጽን፣ የአደባባይ ስብሰባውም ሆነ ሰላማዊ ሰልፉ እውቅና ያልተሰጠው መሆኑን እናስታውቃለን›› በማለት አስፍሯል፡፡

የትብብሩን ሰልፍ እያስተባበሩ ያሉት ፓርቲዎች አመራሮች ዛሬ ለአስተዳደሩ በጻፉት ደብዳቤ እንደጠቀሱት ደግሞ፣ የሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 3/1983 አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ 2 “የከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት በዚህ አዋጅ አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ 1 የተመለከቱትን ሁኔታዎች በማገናዘብ ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ሥፍራ ቢደረግ ይሻላል የሚል አስተያየት ካለው ምክንያቱን በመግለፅ ይህንኑ ጥያቄው በደረሰው በ12 ሰዓት ውስጥ በጽሁፍ ለአዘጋጁ የማሳወቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ ሆኖም የከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው ምን ጊዜም ወይም በየትኛውም ቦታ ሊካሄድ አይችልም ማለት አይችልም” በማለት አስተዳደሩ እውቅና የመንፈግ ስልጣን እንደሌለው ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም፡-
‹‹1ኛ. እውቅና እንዲሰጥ የተጠየቀ ማንኛውም አካል ከላይ የተደነገገውን በማገናዘብ ለሌላ ጊዜና በሌላ ቦታ እንዲደረግ ሃሳብ ከማቅረብ ውጭ ሰላማዊ ሰልፉ ምን ጊዜም ወይም በየትኛውም ቦታ ሊካሄድ አይችልም ለማለት ለመስሪያ ቤታችሁ ስልጣን ያልተሰጠ በመሆኑ፤
2ኛ. ሰላማዊ ሰልፉና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የሚከናወኑት በመሰረታዊነት ለትላልቅ የመንግስትና ዓለም ዓቀፍ ተቋማት ለማሳወቅ በመሆኑ በእነዚህ አካባቢ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ማድረግ በአዋጁ ያልተከለከለ በመሆኑ፤
ለጥያቄያችን የተሰጠን መልስ ከምክንያታዊነትና ህጋዊነት ውጭ ሰልፉ እንዳይካሄድ ለመከልከል ስለሆነ እንዲህ ዓይነቱን ኢ-ህጋዊ የሆነ ውሳኔና አሰራር ፈፅሞ የማንቀበል በመሆኑ አስቀድመን ባሳወቅነው መሰረት ሰላማዊ ሰልፉን በተጠቀሰው ቀን፣ ሰዓትና ቦታ የምናካሂድ መሆኑን እያሳወቅን በጽ/ቤታችሁ በኩል አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግልን በድጋሚ እናስታውቃለን›› ብሏል ትብብሩ ዛሬ ለአስተዳደሩ በጻፈው ደብዳቤ፡፡

 

1255213_621181758007486_3432632376110383431_n


በድቡብ ሱዳን አራት ኢትዮጵያውያን በጥይት ተመቱ

$
0
0

news

በደቡብ ሱዳን በዋና ከተማዋ ጁባ አንድ ወንድና አንድ ሴት ሲገደሉ ሁለት ሴቶች ግን በጠና ቆስለው ወደ ኢትዮጵያ መወሰዳቸውን ኢሳት ወኪሎቹን ጠቅሶ ዘገበ። የሁለቱም ሟቾች አስከሬንም በኢትዮጵያውያን እርዳታ ወደ ኢትዮጵያ መሄዱ ታውቆል:: ሰዎቹ በምን ሁኔታ እንደተገደሉና እንደቆሰሉ
እንዲሁም ጥቃቱን ያደረሱትን ወገኖች ዝርዝር ለማወቅ አልተቻለም ያለው ኢሳት በደቡብ ሱዳን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ በኢትዮጵያውያን የሚደረገውን ግፍና እንግልት ከመከታተል ይልቅ በዶላር ጥቁር ገበያ ምንዛሪ መሰማራቱን የገለጸው ወኪላችን ፣ የቀድሞ የህወሃት ባለስልጣናት በጁባ ከተማ የሚያራምዱትን የቢዝነስ ተቋምና በጋምቤላ በኩል የሚያመጡትን የጤፍና የተለያየ ሸቀጣሽቀጥ ንግድ ጉዳይ ቅድሚያ በመስጠት አብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚያቀርቡትን አቤቱታ እንደማይሰማ ተናግሯል። ለህወሃት አባሎች ህጋዊ የመኖረያ ፈቃድና የንግድ ፈቃድ ለማስወጣት የጁባ ባለስልጣናትን ደጅ የሚጠናው ኢምባሲው ምርቶችን ወደ ደደቡብ ሱዳን በማስገባት በኩል ወኪል ሆኖ እየሰራ መሆኑን ጠቅሷል።

የድምፃችን ይሰማ ወቅታዊ ጽሁፍ: ለህገወጥ በደል እምቢተኝነት በራሱ ታላቅ ድል አይደለምን?

$
0
0

ማክሰኞ ህዳር 23/2007

ሙስሊሙ ማህበረሰብ ሰላማዊ የመብት ትግል ከጀመረ አንስቶ ከመንግስት የሚሰነዘርበትን በርካታ ጥቃቶች ተቋቁሞ አሁንም ድረስ በትግል ላይ ጸንቶ ቆይቷል፡፡ ሰላማዊ ትግል በባህሪው የሚወስደው ጊዜ ሊያጥርም ሊረዝምም እንደሚችል ታሪክ የሚመሰክር ቢሆንም ህዝበ ሙስሊሙ መጀመሪያውኑም ወደ ትግሉ ሲገባ በአጭር ጊዜ የሚገኝ ድል እንደሌለ አምኖበትና አውቆት እንደሆነ እሙን ነው፡፡ ትግሉ በተጠነሰሰበት አወሊያ በየሳምንቱ ጁሙዐ እየተሰባሰበ ሃሳብ በሚለዋወጥበት ወቅት እንኳን ትግሉ ሊረዝም እንደሚችል እና ፈታኝም እንደሚሆን ቀድሞውኑ በቅጡ ተረድቶ ነበር፡፡ በየትኛውም የትግል ሂደት ከዋናው ድል በፊት የሚመጡ በርካታ ድሎች እንደሚኖሩም በሚገባ ተረድቷል፡፡ ለዚያም ነው በትግሉ ርዝመት ሳይሰላች መንገዱ ላይ ያገኛቸውን ድሎች እያስጠበቀ በትግሉ ሀዲድ ላይ መጓዙን የቀጠለበት፡፡ ከእነዚህ በሂደት ከተገኙ የድል እሴቶች መካከል ደግሞ የህዝበ ሙስሊሙ ለበደል እምቢተኛ መሆን አንዱ ነው፡፡
EthiopianMuslimsProtest
ህዝበ ሙስሊሙም ሰላማዊና ህገ መንግስታዊ መብቱን ሲጠይቅ ከመንግስት በኩል እየተፈፀመበት ያለውን ዘርፈ ብዙ ጥቃት ተቋቁሞ በትግሉ መስመር ላይ ቀጥ ብሎ ተገኝቶ ለህገወጥ በደል እምቢተኝነቱን ማሳየቱ በሀገራችን የሰላማዊ ትግል መድረክ ልዩና ደማቅ ታሪክ አስመዝግቦለታል፡፡ ግና መንግስት ትግሉ ሰላማዊና ህገ መንግስታዊ መሆኑን እያወቀ ሆን ብሎ አሰቃቂ እርምጃ እየወሰደ የህዝቡን ሞራል ለመስበርና ከትግሉ እንዲወጣ ለማድረግ ሞከረ፡፡ ህዝቡ ግን አሁንም ድረስ ‹‹እምቢ ለመብቴ! ዲኔ ከሌለ እኔ የለሁምና የሚመጣውን እቀበላለሁ!›› በሚል ወኔና እምቢተኝነት ተንቀሳቅሷል፡፡ የሚጠበቅበትን መስዋእትነትም ከፍሏል፡፡

በቅርብ ዓመታት በታዩ የአገራችን ማህበረ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ውስጥ መንግስት መፍትሄ ያልሰጠው አንዱ ትልቁ ጉዳይ ይኸው የህዝበ ሙስሊሙ የሃይማኖት መብት ጥያቄ መሆኑንም መንግስት ራሱ ሊከደው ያልቻለው እውነታ ነው፡፡ ይኸው ህዝብ ጥያቄው ሳይመለስለት ወደኋላ እንደማይልም ከማንም በላይ መንግስት ራሱ ያውቀዋል፡፡ ህዝበ ሙስሊሙም አሁንም ድረስ የተለያዩ አጋጣሚዎችን በመጠቀም እምቢተኝነቱን በተግባር እያሳየ ነው፡፡
አዎን! መብትን አሳልፎ አለመስጠት (እምቢተኝነት) ለዋናውና ትልቁ ድላችን መዳረሻ እንደ አንድ ዋነኛ ግብዓት ተደርጎ የሚወሰድ ነውና ህዝበ ሙስሊሙ በመንግስት ጥቃቶች ሳይደናገጥ በዚሁ ህዝባዊ ፅናት ላይ መገኘቱ ድሉ ከሚገመተው በላይ ቅርብ ለመሆኑ አመላካች መሆኑ አያጠራጥርም፤ ድልም ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለምና!!!

ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

ግንቦት 7 “ተማሪዎች፣ መምህራን እና የተቋማት ፕሬዚዳንቶች ለአመጽ ተነሱ”አለ

$
0
0

በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አቋሙን በሚገልጽበት ር ዕሰ አንቀጽ ግንቦት ሰባት የፍትህ የነፃነት ንቅናቄ ” ተማሪዎች፣ መምህራን እና የተቋማት ፕሬዚዳንቶች ለአመጽ ተነሱ” አለ:: ሙሉውን የግንቦት 7 ወቅታዊ መል ዕክት እንደወረደ ይኸው:-

Ginbot-7-Top-logo_4
ዘረኛውና አምባገነኑ የህወሓት አገዛዝ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ከካድሬ ማሰልጠኛ ማዕከላትነት ለይቶ የማያይ ስለመሆኑ በተቋማቱ ውስጥ የሚደረጉ ተግባራት ማረጋገጫዎች ናቸው። ለዚህ ተግባሩ በሰነድ ደረጃ መቅረብ ከሚችሉት የቅርብ ጊዜ ማስረጃዎች ዋነኛው በህዳር 2007 ዓ.ም. በሥራ ላይ የዋለው “የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢህአዴግ የምርጫ ድል ልማት ሰራዊት ግንባታ አደረጃጀት ማንዋል” የተሰኘው በትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላለፈው ሰነድ ነው። ይህ ሰነድ፣ የህወሓት አሳፋሪ የትምህርት ፓሊሲ ባፈጠጠ መልኩ የተገለፀበት፤ የኢፌዴሪ መንግሥት ተብሎ በሚጠራው የህወሓት አገዛዝ ተቋም እና በህወሓት/ኢህአዴግ ፓርቲ መካከል ለይምሰል እንኳን ልዩነት አለመኖሩ በግላጭ የሚታይበት ሰነድ በመሆኑ በዚህ ርዕሰ አንቀሳችን በስፋት ልንዳስሰው ወስነናል።

ሰነዱ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ መርዙን መርጨት የሚጀምረው ገና በመግቢያው ስለማንዋሉ አስፈላጊነት ሲገልጽ ነው። ማንዋሉ “ከምንም በላይ የብጥብጥና የሁከት መንስኤ የሆነውን ተማሪ በኢህአዴግ አመራር አባላት እየታገዙ ለመያዝ የሚያስችል ነው” በማለት ህወሓት ተማሪውን የሚመለከተው “ከምንም በላይ በብጥብጥ መንስኤነት” መሆኑ፤ ለዚህ መድሀኒቱ ደግሞ ተማሪውን በኢህአዴግ አመራር አባላት “መያዝ” መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ይገልፃል። ቀጥሎም “በምርጫው ሊፈጠር የሚችለውን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሁከትና ብጥብጥ ለማስቆም በማደራጀት መረጃ ለመጥለፍ አመችነቱ የላቀ እንደሚሆን ታምኖበታል” በማለት መረጃ መጥለፍ የዩኒቨርስቲዎችና የትምህርት ሚኒስቴር ሥራ እንደሆነ አድርጎ ያቀርባል።
Ginbot_7_Logo_L
የማንዋሉን ዓላማዎች በሚገልፀው ክፍል ደግም “… የከፍተኛ ትምህርት የትምህርት የልማት ሰራዊት ግንባታን ወይም የፓለቲካ ሰራዊት ግንባታ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተደራጀና በተናቀጀ ሁኔታ በማቀጣጠልና በማስቀጠል … ምርጫ 2007 ውጤታማ ለማድረግ እና የኢህአዴግን አሸናፊነት ለማረጋገጥ ነው” በማለት ተቋማቱን የኢህአዴግ የምርጫ መሣሪያ መሆናቸውን፤ ግባቸውም የኢህአዴግ አሸናፊነትን ማረጋገጥ መሆኑ ይገልፃል።

በገጽ 3 ላይ ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች “በኢህአዴግ ላይ ያላቸው አቋም የወረደ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በማንኛውም ተቃውሞ ድምፅ ከተጠሩ፤ ሰልፍ የሚያደምቁ፤ ተቃውሞን ከግብ ለማድረስ ሁነኛ መሳሪያ ናቸው። ተማሪዎች በየትኛውም ሐገር እንደታየው አደባባይን የመያዝ ህዝብን አስተባብረው ለተቃውሞ የማሳደም እድላቸው የሰፋ በመሆኑ ከዚህም ሲያልፍ፤ የኢህአዴግ ምከታን በመቃወም ለጠላት ጎራ ተሰልፈው የመታጠቅ እድላቸው ከፍተኛ ነው” ሲል “በወጣቱ እጠላለሁ” የሚለው የህወሓት/ኢህአዴግን ስጋት አፍረጥርጦ ያወጣል። ትንሽ ወረድ ብሎ ደግሞ “በተለይ በአሁኑ ሰዓት ፈተና ላይ የጣለን የምርጫ ጉዳይ እንደምናሸንፍ ቃል የተያዘለት ቢሆንም፤ ፈተናዎች የሚፈጠሩት በህዝብ እና በራሱ ታማኝ ባልሆኑ ሃይሎች ማለትም በመንግስት ክንፍ አይቀለበስም ብሎ ማሰብ አይቻልም። በዚህም ቀድሞ መዘጋጀት ያለበት እና ለሁከት እና ለብጥብጥ መሳሪያ ሊሆን የሚችለው የህዝብ ክንፍ የተማረው ሃይል ሊሆን ስለሚችል ሊታሰብበት ይገባል” ሲል በተማረው ወጣትና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሠራተኞች ላይ ያለው ጥርጣሬና ፍርሃት ምን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ ይገልፃል።

የ2007 ምርጫ በህወሓት ሹማምንት ላይ የፈጠረውን ጭንቀት በዚህ ሰነድ ላይ በገሀድ የሚታይ በመሆኑ እያንዳንዱ ዓረፍተ ነገር በጥንቃቄ ሊነበብና ሊተነተን የሚገባው ነው። ለምሳሌ በገጽ 6 ላይ ስለዩኒቨርስቲ ተማሪ ሲገልጽ “የአመፅ እና የብጥብጥ መነሻ ሊሆን የሚችል ሀይል መሆኑን በአክራሪዎች ሲጠለፍ፤ ከመንግስት ሃይማኖቱን እየመረጠ በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ፤ በጅማ ዩኒቨርስቲ፤ በመቀሌ ዩኒቨርስቲ እና በሌሎችም ትምህርቱን ትቶ ሲኮበልል ተመልክተናል” ይላል። ለተማሪዎች፣ ከመንግሥት እና ከሃይማኖት አንዱን እንዲመርጡ ተደርጎ ሃይማኖታቸውን የመረጡ መኖራቸውን እና ይህ ደግሞ አደገኛ ነገር መሆኑን ነው ይህ ዓረፍተ ነገር የሚነግረን። ለመሆኑ ይህ ምን የሚሉት ምርጫ ነው? በእንዴት ያለ ሥርዓት ነው ዜጎች ከመንግስትና ከሃይማኖት አንዱን ምረጡ የሚባለው? እንዲህ ዓይነት ምርጫ ቀርቦ ሃይማኖትን መምረጥ እንዲህ ክፉ ነገር የሆነው ለምንድነው? ይህ ጉዳይ ብቻውን ብዙ የሚያነጋገር ነገር አለው።

በገጽ 8 ላይ ደግሞ “ከፍተኛ አመራሩ ተቋማዊ ለውጥ እንዲሁም የትምህርት ልማት ሰራዊት ግንባታ ቴክኒካዊ ሳይሆን ፓለቲካዊ ጉዳይ መሆኑን ተገንዝቦ ካለእርሱ ባለቤትነትና ቀጥተኛ ተሳትፎ ሰራዊት መገንባት እንደማይቻል በመገንዘብ የመሪነት ሚናውን ካለምንም ማወላዳት መወጣት ይጠበቅበታል” በማለት እየተሠራ ያለው የፓርቲ ወገንተኛ የሆነ ፓለቲካ መሆኑን ብቻ ሳይሆን የትምህርት ተቋማት መሪዎች ዋና ተልዕኮ ትምህርት ማስተማር ሳይሆን የወያኔ ፖለቲካን ማስፈጸም መሆኑን ምንም ሳይጎረብጠው ፍርጥርጡን ያወጣዋል። ትንሽ ወረድ ብሎም “የጋራ መግባባት የምንለካው በመጀመሪያ ለምርጫው የኢህአዴግ የድጋፍ የድል ሰራዊት ብዛት ነው” በማለት ከላይ ያለውን በማጠናከር ወገንተኛነቱም ለኢህአዴግ መሆኑ ያውጃል። በመጨረሻም “ … ሁሉም የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ውጤታቸው የሚሞላላቸው ለምርጫው በሚያዘጋጁት የድጋፍ ሃይል ይወሰናል” በማለት የአካዳሚ ነፃነት ብቻ ሳይሆን የከፍተኛ ትምህርት ሥርዓትን ለቀብር ያዘጋጃል።

ይህ ነው የህወሓት የትምህርት ፓሊሲ! የዩኒቨስቲዎች ቁጥር ለማመን በሚቸግር መጠን ቢጨምር፤ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ቅበላ በብዙ መቶኛዎች ቢያድግ ጥቅሙ ምኑ ላይ ነው። በእንዲህ ዓይነቱ ፓሊሲ ከተገነባ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋም ይገኛል የምንለው ፋይዳ ምንድነው?

ህወሓት በገሀድ በጠላትነት የፈረጃቸው የአገራችን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ መምህራንና ሠራተኞች ይህንን አሳሳቢ ጉዳይ በአጽንኦት እንዲመለከቱ ግንቦት 7፣ የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ያሳስባል። ትውልድንም የትምህርት ሥርዓቱንም የማዳን ግንባር ቀደም ኃላፊነት በተማሪዎችና በመምህራን የወደቀ ሸክም ነው ብሎ ግንቦት 7 ያምናል። መላው የትምህርት ሥርዓት ለአንድ ፓርቲ የምርጫ ውድድር መሣሪያነት ሲውል ማየት እና የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች የሥራ አፈፃፀም የሚወሰነው ለገዢው ፓርቲ ባስገኙት ድምጽ ብዛት ነው መባሉ፤ እነሱም ይኸንን ተቀብለው መሥራት መቀጠላቸውን የመሰለ አሳፋሪ ነገር በአካዳሚያ ውስጥ የለም። የከፍተኛ ትምህርት ተቋሞቻችን ይህን ውርደት መቀበል የለባቸውም። ሰነዱ ህወሓት ከፍተኛ ትምህርትን የሚመለከትበት ዕይታ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነውና ለምርጫ ወቅት ብቻ የተዘጋጀ የአጭር ጊዜ መመሪያ ተደርጎ መወሰድ የለበትም። ይህ ሰነድ ህወሓት፣ ተማሪዎችንና መምህራንን እንደጠላት፤ ተቋማቱን ደግሞ ጠላትን እንደመቆጣጠሪያ መሣሪያ እንደሚመለከት፤ ይህ ዕይታው ደግሞ ቋሚ መሆኑ በግልጽ ያሳያል። በህወሓት ዕይታ ከተገነቡ ተቋማት ምን ዓይነት ትምህርት ይገኛል?

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የትምህርት ኃላፊዎችና ፕሬዚዳንቶች ሆይ! ለገዛ ራሳችሁ ክብር፣ ለአካዳሚ ነፃነት፣ ለትውልድ ስትሉ በዚህ መመሪያ ላይ አምጹ! “እንቢ፣ አሻፈረን፣ በዚህ መመሪያ አንገዛም” በሉ! የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጎናችሁ ይቆማል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

ይድረስ ለጎንደር ሕዝብ

$
0
0

ቁ. 2

በተለያዩ ዘመናት በአገራችን ወደ ሥልጣን የመጡት ገዥዎች፤ ሕብረተሰባችን ከፋፍሎ ለመግዛት እንዲያመቻቸው የዘር ግንድ እየቆጠሩ አንዱን ከሌላው የተሻለ አስመስሎ በመሳል፤ አንደኛውን በሌላኛው ወግን ላይ በስነልቦና ቂም እያናከሱ፤ የግፍ ግዛት ዘመናቸውን አሳልፈው አሁን ከአለንበር ዘመን ደርሰናል። በአሁኑ ጊዜ በሥልጣን ላይ የተፈናጠጠው መንግሥት ደግሞ ገና ከጅምሩ ወደ ሥልጣን ሲመጣ በረቀቀ ተንኮል የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘር ሐረግ ከፋፍሎ ለመግዛት እንዲያመቸው አንቀጽ 39ኝን በሕገመንግሥት አጽድቆ ለረዥም ዘመን በጋራ ሕብረተስባዊ ገመድ ተሳስረው የኖሩትን ኢትዮጵያዊያን በጎሳ በመከፋፈል በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች ያሉ ብሔረሰቦች ተፈጥሮአዊ የሆነውን እና ሊከባበሩበት የሚገባውን ማንነታቸውን ጦርና ጋሻ አድርገው እንዲዋጉበት በማድረግ ነው የሥልጣን እድሜውን እያራዘመ ያለው።

(ጎንደር ፋሲል ግምብ - ፎቶ ፋይል)

(ጎንደር ፋሲል ግምብ – ፎቶ ፋይል)


ታዲያ ይህ መንግሥት ለአገራችን ሰላም ያመጣል በሚል ከፋፍሎ ለመግዛት እራሱ በቀመረው የጎሳ ክልል ቀቢጸ ተሥፋ “በብሔሮች” ራሥን በራሥ የማሥተዳደር ሥም፤ አብሮ የኖረውን እያራራቀ፤ ተፈቃቅዶ ይኖር የነበረውን እንደጠላት እያሥተያዬ፤ አካባቢያዊ ሰላምን እያደፈረሰ፤ እርሥ በርሥ እያጋደለ ያለው ትልቁ ችግር በአገራችን ላይ የተደነገገው ህገመንግሥታዊ አደጋ፤ ከሃያ ሦስት ዓመት በኋላ ህግ አውጭውን አካል እና መንግሥታዊ መዋቅሩን በማሥጨነቅ እርስ በራሱ ሲያተራምስ እያየን ነው። በመሆኑም፤ ባለፈው ሚያዝያ ወር ባወጣነው እና በድህረ-ገጽ ለማሳነበብ እንደሞከርነው ሁሉ፤ አሁንም በድጋሚ የምናሥገነዝበው፤ መንግሥታት መጥተው፤ መንግሥታት ሲያልፉ፤ የማያልፈውን የቅማንት እና የአማራ ህብረተሰቦች የጋራ ታሪክ ዘመኑ ባመጣው የጎሳ ፖለቲካ ጉንፋን መሰል አሥተሳሰብ እና ድርጊት የኋላ ታሪካቸውን ማጥቆር እና የወደፊቱንም ማህበራዊ ግንኙነታቸውን ማጨለም አይገባም እንላለን።
ሰለዚህ ይህን አገር አፍራሽ፤ ሰላም አደፍራሽ የሆነውን አንቀጽ 39ኝን እንደ መብት ማስከበሪያ በመጠቀም የቅማንት የማንነት እና ራሥን በራሥ የማሥተዳደር ጥያቄ ያነሱ የቅማንት ተወላጅ ወገኖቻችን ያልተገነዝቡት ነገር፤ ተዋልዶና ተጋብቶ፤ አንድ ሐይማኖት አምልኮ ለረዥም ዘመን ከኖረው ወገናቸው ጋር አብሮ የማያኗኑር መሆኑ ነው። ቅማንት እና አማራ ጊዜ እና ቦታ አንድ ላይ ያሥቀመጣቸው ብቻ ሳይሆኑ፤ እጅግ ብዙ የጋራ ችግር እና ደሥታን ጽዋ አብረው የተጎነጩ፤ ረዥም የታርክን ጎዳና አብረው የተጓዙ፤ እምነትና ቋንቋ ባንድ ገመድ ያስተሳሰራቸው ሕዝቦች መሆናቸውን ነው። ይህ ሲባል ግን፤ መለሥተኛ ችግሮች ተከስተው አያውቁም ማለት አይደለም። በሁለቱ ህብረተሰቦች መሃከል የነበረው ችግር ግን፤ በሁለት ወንድማሞች መካከል ከሚከሰት ችግር የተለዬ አልነበረም። ስለሆነም ነው በየጊዜው የሚፈጠሩ መለሥተኛ ችግሮቻቸውን በጋር እየፈቱ እና መቻቻልን መሰረት አድርገው የአንድነታቸውን ታሪክ ጠብቀው ከዚህ የደረሱት። ወደፊት ማደግና መቀጠልም ያለበት በዚሁ መንገድ ነው። ይህ ደግሞ በማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ያለ እና የሚኖር ነው።
ይህን ሥንል ግን፤ የቅማንት ብሔረሰብ ወገኖቻችን ይህን ጥያቄ ያለ ብሶት አነሱት በማለት በጭፍን ለመኮነን አይደለም። ሆኖም፤ በኛ እይታ፤ አሁንም በድጋሚ ማሥገንዘብ የምንፈልገውው፤ ችግሩ የመልካም አሥተዳደር በደል እንጂ፤ ለቅማንቱ ችግር ምንጭ አማራው አይደለም። ለአማራውም ችግር ምንጭ፤ ቅማንቱ አይደለም። ይህ የአሥተዳደር በደል ቅማንቱ ራሱን ሥለከለለ ይፈታል ብሎ ማሰብ፤ እጅግ ሥህተት ነው። በመላ አገሪቱ የተንሰራፋው የአሥተዳደር በደል፤ በመላ አገሪቱ ሳይፈታ፤ ለአንድ ጎሳ ብቻ ነጻ እና ዲሞክራሲያዊ መብት እንደ መና ከሰማይ ሊወርድ አይችልም። እሁን እዬተሄደበት ባለው መንገድ ሊመጣ የሚችል ለውጥ ቢኖር፤ በአካባቢው ባልተወለዱ ባልሥልጣኖች ከመበዝበዝ ይልቅ፤ ከራሳችን በተወለዱ መሪዎች መበዝበዝን ነው። ምክንያቱም በዬትኛውም የአገራችን የጎሳ ክልልን እንደ ነጻነት ቆጥረው በተግባር ለማዋል የሞከሩት አካባቢዎች ያተረፉት ሃቅ ይህ ሲሆን አይተናል እና።

ስለሆነም፤ በሰሜን አሜሪካ የምንኖር ጉዳዩ ያገባናል የምንል የቅማንት ብሔረሰብ ተወላጆች፤ በአገር ቤት የተወሰኑ የቅማንት ተወላጆች፤ ያነሱት የማንነት እና የራሥን በራሥ ማሥተዳደር ጥያቄ አለመመለሥ ምክንያት በተወሰኑ ግለሰቦች መካከል እርሥ በርሥ መተነኳኮስ መጀመሩን ሰምተን እጅግ በጣም አዝነናል፤ ቀጣዩም አሳስቦናል። የዚህን ጥያቄ አደገኛነት ባለፈውም ጠቁመናል፤ እሥከ የት ሊዘልቅ እንደሚችልም አመላክተናል። አሁንም በድጋሚ ያለፈውንም ሆነ የወደፊቱን የጋራ ባህላችን እና የጋራ አካባቢያዊ የኑሮ ዘይቤ አበላሽቶ እና መጥፎ አሻራ ጥሎ የሚያልፍ መሆኑ መገንዘብ ያስፈልጋል።

አሥተሳሰቡ እና ድርጊቱ፤ ሁሉንም የሕብረተሰብ አባሎች የማይወክል እንደሆነ ብናውቅም፤ የሁኔታው መከሰት ግን፤ በራሱ አሥደንጋጭ እና አሳዛኝ፤ እንዲሁም አሳፋሪም ጭምር ነው። ይህ የወያኔ/ኢህአዴግ መንግሥት ባመጣው የጎሳ ወጥመድ ውስጥ የገቡ ወገኖች የሚያራምዱት አስተሳሰብ አስከፊ ውጤት ሊሆን የሚችለው፤ መንግሥታት መጥተው፤ መንግሥታት ሲያልፉ፤ የማያልፈውን የሁለቱ ህብረተሰቦች የኋላ ታሪካቸውን ማጥቆር እና የወደፊቱንም ማህበራዊ ግንኙነታቸውን ማበላሸት ብቻ ነው።

እንዲህ አይነቱ ለማንም ወገን የማይጠቅም ልብ የሚኢያሻክር ድርጊት በአስቸኳይ መቆም አለበት። ይህን በማለታችን እንደ ድፍረት ሊያሥቆጥርብን አይገባም። እኛም ለተወለድበት አካባቢ፤ ለተፈጠርነበት ህብረተሰብ የሚበጀውን የቅርብ እና የሩቅ ራዕይ የማመላከት ግዴታ አለብን እና። ይሁንና፤ በሁለቱ ሕዝቦች ውሥጥ የሚገኙ ሽማግሌዎች፤ አዋቂዎች፤ እና ምሁራን ሁኔታውን አግባብ ባለው እና በሰከን መንገድ ይፈቱታል ብለን እናምናለን። ከሁሉም በላይ የአካባቢውን ሰላም እና መረጋጋት ታሳቢ አድርገው በሁለቱ ህብረተሰቦች መሃከል ሰላማዊ ንግግር ተጀምሯል የሚል ሰምተናል። ይህ ጅምር ከወዲሁ የሚበረታታ ሲሆን፤ የጋራ ወገኖቻችንን የቆዬ ፍቅር የሚያረጋግጥ ክሥተትም ጭምር በመሆኑ፤ ጠንክሮ እንዲቀጥል በአክብሮት እናሳሥባለን። እኛም የአብሮነት ሂደቱ እና በአካባቢው ሰላማዊ ኑሮ እንዲቀጥል የምንችለውን ሁሉ ለመተባበር ዝግጁ ነን።

በተጨማሪም፤ ማንኛውም ግለሰብ፤ ቡድን፤ ድርጅትም ሆነ የመንግሥት አካል በሥሜት ተገፋፍቶ እና ባለማወቅ ወይም ሁኔታውን ለተለዬ የግል አላማ አሥቦ የሚንቀሳቀስ ቢኖር፤ “አንተ ሰላም እንድትውል ጎረቤትህ ሰላም ይሁን” እንዲሉ፤ የሚፈጠረው የሰላም መደፈረስ ሁሉንም የሚጎዳ በመሁኑ ከመጥፎ ተግባር እንዲቆጠብ ለማሳሰብ እንወዳለን። ህዝቡም፤ የላይ የታች ሳይባባል በአንድ ሆኖ ለጥፋት የሚንቀሳቀሱትን ትክክል አደላችሁም ማለት የሚገባ መሆኑን ጊዜው እያመላከተ ነው። አገር በሰነፎች እንደማይገነባ ሁሉ፤ ሰላምም በነገረኞች አይረጋም እና።

በዚህ አጋጣሚ ሁለቱም ህዝቦች መገንዘብ ያለባቸው አጠቃላይ ሁኔታውን እና የሰሞኑንም ቤተሰባዊ አለመግባባት የፈጠረው የመንግሥት ፖሊሲ እና አሰራር መሁንን ነው። “ውኃው ሂያጅ ደንጊያው ቀሪ” እንደ ሚባለው ሕዝብ ይኖራል መንግሥት ግን ያልፋልና። የሚያልፍ መንግሥት ዘላለማዊ የሚኖር የታሪክ ጠባሳ ጥሎ እንዳያልፍ መጠንቀቅ አስፈላጊ ነው። እያንዣበበ ያለው ችግር ከፍ ሲል የኢትዮጵያ ዝቅ ሲል ደግሞ የጎንዳር ሕዝብ ችግር ነውና አብረን ተባብረን ወደ ሰላም እና የዘር ክልል ያልበከለው ሁለንተናዊ የአንድነት ወንድማማቻዊ ጎዳና እንምራው።

በመጨረሻም፤ “እርቅ፤ ደም ያደርቅ” እንዲሉ፤ የተጣላውን እያሥታረቀ ለዘመናት ራሱን ጠብቆ የኖረ ህዝብ፤ ዛሬም የገጠሙትን ችግሮች በለመደው ባህላዊ የሽምግልና ጥበብ እየፈታ ወደፊት እንዲቀጥል ጥርጥር የለንም። ለሁሉም ወግኖቻችን እና ሕዝባችን፤ ሰላሙን እና ደህንነቱን የምንመኘው ከልብ ከሚመነጭ ፍቅር እና አክብሮት ጋራ ነው።

ጉዳዩ ይመለከተናል ከምንል የቅማንት ብሔረሰብ ተወላጆች፤ ሰሜን አሜሪካ።

በቅርቡ ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች በፅጥታ ሀይሎች ታፍነው ከተወሰዱት የአንድነት አባላት አራዳ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ታወቀ

$
0
0

ዛሬ ህዳር 23 በ8 ሰዓት የአንድነት ታሳሪዎች በአራዳ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ!

ethiopia-trial1-300x235በቅርቡ ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች በፅጥታ ሀይሎች ታፍነው ከተወሰዱት የአንድነት አባላት ውስጥ አንጋው ተገኝ፣ እንግዳው ዋኘው፣ በላይነህ ሲሳይ፣ አለባቸው ማሞ እና ሺሻይ አዘናው አራዳ በሚገኘው ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፤ በቦታው ተገኝተን ያለንን አጋርነት እናሳይ።
በፀጥታ ሀይሎች ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ እስካሁን ድረስ የት እንዳሉ ያልታወቁ ሌሎች ታሳሪዎች ደግሞ አባይ ዘውዱ፣ አለበል ዘለቀ፣ ጥላሁን አበበ እና ወጣት አወቀ ብርሃን ናቸው። መንግስት እነዚህን ዜጎች ያሉበትን እንዲያሳውቅና በፍርድ ቤት ቀርበው የዋስትና መብታቸውን እንዲጠበቅላቸው አሁንም ደግመን እንጠይቃለን።

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ

የጽዮንን በዓል አክብረው ከተመለሱ ምዕመናን ውስጥ መኪና ተገልብጦ የአራት ሰዎች ሕይወት አለፈ

$
0
0

ከዘመድኩን በቀለ

በየዓመቱ ህዳር 21 ቀን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት የሚከበረውን የህዳር ጽዮን በዓል ለማክበር ከአዲስ አበባ ተነስቶ የነበረው የአቡነ አሮን መንፈሳዊ የጉዞ ማኅበር መኪና 60 ተጓዥ ምእመናንን ይዞ ከበዓሉ መልስ ዛሬ ከወልድባ ሰቋር ጉብኝት በኋላ ወደ ጎንደር በመመለስ ላይ ሳለ ከአንባ ጊዮርጊስ ወጣ ብሎ ልዩስሙ 44 ተብሎ ከሚጠራው ሥፍራ ላይ አደጋ ደርሶበት ብዙ ሰው ተጎዳ ።
axum
በአደጋው እስካሁን 3 ተጓዥ መንገደኞች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን ቁጥራቸው በዛ የሚሉት ደግሞ ቀላልና ከባድ የሆነ ጉዳት ደርሶባቸው በጎንደር ሆስፒታል በሕክምና ላይ ይገኛሉ ።

ከእነዚህ መንገደኞች መሃል በተለይ ዘማሪ ምትኩ በከባድ ጉዳት ውስጥ እንደሚገኝ በአደጋው ሰዓት ወዲያው በመድረስ የሞቱትንም ሆነ የቆሰሉትን ወደ ሆስፒታል የወሰደው የማኀበረ ወይንዬው ሰብሳቢ መ/ር ደረጀ ነጋሽ በስልክ ገልጾልኛል ።

የአደጋው አድራሽ በቅጽል ሰሙ ቀይ ሽብር በመባል የሚታወቀው የቻይና ስሪት የሆነው መኪና ሲሆን የአደጋውን መንስኤ ግን የክልሉ ፖሊስ እያጣራ መሆኑንም ደረጀ አክሎ ነግሮኛል ።

አሁን ይህን ማስታወሻ በመጻፍ ላይ ሳለሁ ደረጀ የሟቾች ቁጥር ወደ 4 ከፍ ብሏል ብሎኛል።

እንግዲህ ምን እንላለን ያረፉትን ነፍሳቸውን ይማር ።

ማኅበረ ቅዱሳን የምነቅፍብህ ነገር አለኝ – (ከደብረጊዮርጊስ)

$
0
0

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን! ማኅበረ ቅዱሳን Nov. 23 2014 E.C ላውጣፍ ጽሑፍ መልስ።

ሁሌ እራስን ከፍ ከፍ ማድረግ ብቻ! እንዴት ነው ነገሩ? ቀኝህ የምትሰራውን ግራህ አትይ፣ በስውር ለሰራኽው በግልጽ ጌታ ይከፍለሃል፣ ራሱን ከፍ ከፍ ያሚያደርግ ዝቅ ዝቅ ይላል እየተበለ ሲነገርና ትምኅርት ሲሰጥ ሰምተናል። ይህ ለማኅበረ ቅዱሳን አይሰራም እንዴ ??? ሁል ጊዜ እኔ የምሰራው የጽድቅ ሥራ ነው፣ እኛ ተሳስተን አናውቅም፣ እኛ ከሌለን ቤተክርስቲያን አትኖርም ወዘተ። በተቃራኒው እኛንየተቸ መናፍቅ ነው፣ መናፍቅ ካልሆነ “ተሃድሶ” ፕሮቴስታንት ነው፣ ለጥቅም የቆመ አማሳኝ ነው ወዘተ።
mahibere-kidusan-logo
ግርም ይላል!!! እውነቱን ስንነጋገር ማኅበረ ቅዱሳን የሰራቸው ብዙ ጥሩ ነገሮች አሉ። ግን እነኝህን በጎ ሥራዎች ሊመሰክርለት የሚገባው ራሱ አይደለም። እንዴት ራሱ ሰርቶ ለራሱ ምስክርነት ይሰጣል??? ጥሩ ስለመሥራቱ ሊመሰክሩ የሚገባቸው ሌሎች ናቸው። ደግሞም ጥሩ የሚመሰክሩ እንዳሉም ስህተቱንና
ሊታረም የሚገባውን የሚተቹም እንዳሉና እንደሚኖሩ ማወቅ ያሻል። ነገር ግን እነኝህ ተቺዎች በሙሉ መናፍቃን “ተሐድሶ” ፕሮቴስታንት ወዘተ አይደሉም። ከማኅበሩ ባላነሰ መናፍቃንን ከሚተቹና ጸረ መናፍቅ ነኝም ብዬ አስባለሁ ስው የሚለኝን ባላውቅም። እናም የዚህ ጽሑፍ/ትችት አቅራቢ ጸረ መናፍቅ
ነው።

እንደ እኔ እይታ ምንም እንኳን ማኅበረ ቅዱሳን የሰራቸው በጎ ነገሮች ቢኖሩም ብዙ ሊታረሙና ሊሻሻሉ የሚገባቸው መሠረታዊ ለውጥ ጭምር ሳይቀር ሊያደርግባቸው የሚገቡ ጉልህ ጉድለቶች አሉበት። ለምሳሌ አደረጃጀቱን በተመለከተ የቤተክርስቲያንን ማዕከላዊነት የሚፃረር ነው። ባለፈው በቤተ ክህነቱ
ስብሰባ እንደተገለጸው ሁለት ቤተክርስቲያን ያለ ያህል ቤተክህነትን አክሎ በራሱ መዋቅር ዘርግቶ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በርግጥም ከጥቅሙ ጉዳቱ ማመዘን ብቻ ሳይሆን የተሳሳተም ነው። ሊሆን የሚገባው በየከፍተኛ የትምኅርት ተቋማት ተማሪዎች እንደልባቸው ቤተክርስቲያን እና የቤተክርስቲያን
ትምህርት ስለማያገኙ በዛ ዙሪያ የቤተክርስቲያን ትምህርት ሊያገኙ የሚችሉበትን ሁኔታ ላይ ብቻ መወሰን ይገባዋል ባይ ነኝ። ከከፍተኛ ተቋማት የትምህርት ጊዜ በኋላ ተማሪዎቹ/ተመራቂዎቹ ወደ ሕብረተሰቡ ሲቀላቀሉ እንደማንኛውም የቤተክርስቲያኗ አባል በሰበካ ጉባኤ እና በሰንበት ትምህርት ቤት እየታቀፉ
በሚችሉት ሁሉ ቤተክርስቲያንን ማገልገል ቢችሉ ጥሩ ነው። ከከፍተኛ ትምህርት በኋላ ልክ እንደቤተክህነት ተደራጅቶ የራስ ማኅበርን ስለማጠናከርና የራስን ጉባዔያት ማካሔድ ለዘለቂታው ቤተክርስቲያን የራሷ የሆነውን ማዕከላዊ አመራር እንዳይጠናከር ማድረግ ነው። በገንዘብ፣ በጉልበት፣ በእውቀትና በሚችሉት ሁሉ ሰበካ ጉባዔያትን፣ ሰንበት ትምኅረት ቤቶችን፣ ወረዳ ቤተክህነትን፣ ሃገረ ሥብከትን ብሎም ዋናውን ጠቅላይ ቤተክህነትን እና መምሪያዎችን ማጠናከር እንጂ ለራስ ሌላ ቤተክህነት ሆኖ መንቀሳቀስ ቤተክርስቲያንን ያዳክማል እንጂ አያሳድግም። ሌሎችንም ውሻ በቀደደው… እንዲሉ ተመሳሳይ ማኅበራት እየተፈጠሩ እንዲሄዱና ሁሉም የራሱን ጥቅምና አላማ ላይ እንደልቡ እንዲያተኩር ያደርገዋል። አንድ ብቻ ሳይሆን አስራ አንድ ከዛም በላይ ማኅበራት በዚህ መልክ የመደራጅት መብት አላቸውና። ስለሆነም ማኅበረ ቅዱሳን በእውነት ለቤተክርስቲያን መጠናከር እና እድገት ካሰበ ራሱን ማስተካከል አለበት።

ሌላው የማኅበሩ ስህተት ብዙ ጊዜ አህያውን ፈርቶ ዳውላን የሚሉት አይነት ነው። በቅዱሳን ሥም ተሰባስቦ ስለቤተክርስቲያን ይገደናል ካሉ ግለሰብም ይሁን ድርጅት ወይንም መንግስት በቤተክርስቲያን ይዞታ፣ መብትና ክብር ላይ ጉዳት ሲያደርስ በእኩል ጥብቅናን ለቤተክርስቲያን ማሳየት ይገባል። በዚህ ዙሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ከአሥር ለሚታረም ጥያቄ ሁለት ከአሥር ብቻ ያገኝ ይሆናል። ቅዱሳን እስከ ሞት ድረስ አላውያንን ገሥጸው ለእምነታቸው ምስክር ሆነዋል እንጂ አድርባይና ፈሪ ሆነው ከእምነታቸውና ከኃይማኖታቸው ክብር አጉዳፊዎች ጋር አላበሩም። የቤተክርስቲያኗ ታላቅ ገዳም ሲደፈር ገዳማዊያኑ የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ፣ አላውያን መሪዎች ቤተክርስቲያንን ሲያንንቋሽሹ እና አከርካሪውን ሰብረነዋል በማለት ሲያላግጡ እንደ አንድ ትልቅ የቤተክርስቲያን ማኅበር እንዴት ዝም ይባላል? ይህም ወይ እንደ እስክንድር ተዋጋ ወይ የእስክንድርን ስም መልስ የሚለውን አባባል ያስታውሳል።

ሦስተኛው የማኅበረ ቅዱሳን ስህተት ከላይ የተጠቅስው የአደረጃጀት ውጤት ያስከተለው ነው። ይህም ለቤተክርስቲያን ዘላቂና መሠረታዊ የሆኑ ተቋማትን በጥራት ከመስራትና ለቤተክርስቲያኗ እድገት አስተዋስዖ የሚያደርጉ ሥራዎች ላይ ከማተኮር ይልቅ ለራስ/ለስጋ የሚመቹ የጽ/ቤት ግንባታዎች እና የንግድ ሥራዎች ላይ ማተኮሩ ቆሜለታለሁ ከሚለው መንፈሳዊ አገልግሎት በተለይም ጠበቅ ያለ የክርስትና ሕይወት ነው የምንመራው እንዲሉ ከሆኑት አባላቱ ሁኔታ ጋር ፈጽሞ የተለያየ ነው። ጽድቅ ከራስ ቆርሶና ራስን ጎድቶ ለሌላው እንደራስ አስቦ የራስን እንኳን አካፍሎ የሚገኝ ወይንም የሚኖር ሆኖ ሳለ የግሉ ቀርቶ በጋራ እንኳን ለሚደረገው ነገር ቅድሚያ ለእኛ በሚል አካሔድ የትም ወድቀው ለሚታዩት ወገኖች የሚረዳ ጓለማውታ፣ የአረጋውያን መጦሪያ፣ የእኔ ብጤ ልጆች ማስተማሪያና ማሳደጊያ ከመሥራት ይልቅ ለራስ የሚመቹ ነገሮችን ማስቀደሙ ማኅበሩን የሚያስተቸው ነው። ከዚህም ሌላ ቤተክህነቱ ሊሰራው የሚገባውን ሥራ እንዳይሰራና ፍፋላፊነቱን እንዳይወጣ መሻሻል እንዳያሳይ ተጽ እኖ ያደርጋል።

እንደቤተክህነት ደመወዝ ከፋይ መሆን ያውም ያለ ቤተክርስቲያኗ ገቢና ወጪ ካርኒ ወጪ ለራስ ደጋፊዎችን ለማከማቸት ካልሆን በስተቀር ለቤተክርስቲአን እድገትና ለውጥ አያመጣም። እድገት የሚያመጣው የቤተክህነቱን አድባራትና ገዳማት መምሪያ ማጠናከ ነውና። አራተኛው ስህተት ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ይመለከታል ። መቼም አሁን ይህ የቤተክርስቲያን ሥርዓት እንዲህ ሆኖ ቢሻሻል ይሻላል ቢባል ይኼማ መናፍቅ ነው ተሃድሶ ምናም ነው እንደሚባል አልጠራጠርም።

እውነታው ግን አንዳንድ የማኅበሩ አባላት የሆኑ ሰዎች ከተለምዶው/ ከቀኖና ቤተክርስቲያን ውጪ ዲያቆናት፣ ቀሳውስት ሲሆኑ እናያለን እንሰማለን። መሆናቸው ብቻ ሳይሆን የሚገርመው የሆኑትን ሆነው ለመገኘት ብዙም ጥረት ሲያደርጉ አለመታየታቸው ነው። አንዳንዴም በድፍረት ያልተማሩትን እና
የማያውቁትን ሙያ በሚያሳፍር መልኩ በአደባባይ ሲያበላሹ ይስተዋላሉ። ይህም ሊታረም የሚገባው ነው።

ሌላውና ትልቁ የማኅበሩ ድክመት ደግሞ በቤተክርስቲያን ጉዞ ውስጥ በየዘመኑ የሚፈጠሩ ፈተኛዎች እና ውጣ ውረዶች መኖራቸው እየታወቀ ልክ ዛሬ የመጡና የተፈጠሩ ይመስል ትናንሽ ነገሮችን ከሚገባው በላይ በማጋነን፣ ባለማወቅና በተለያዩ ምክንያቶች የንጽህት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንን አስተምህሮ
ባለመረዳት ከቤተክርስቲያኗ አስተምህሮና ይትባሃል የሚወጡትን በፍቅርና በጥበብ ወደ ቤተክርስቲያኗ ከመመለስ ይልቅ አጋኖ አጋኖ እንዳልነበሩ ማድረጉ ነው። ይህም አንቺ ማነሽና ማንን ታሚያለሽ ያሰኘዋል።

ለምሳሌ ኦርቶዶክሳዊ መዝሙራትን በተመለከተ ያለውን ክፍተት በመሙላት ለምእመናኑ አማራጭ ከማቅርብ ይልቅ ያለውን ክፍተት የተገነዘቡ በክፍተቱ ለመጠቀም እና ያለባቸውን ሥጋዊ/ የኑሮ ችግር ለማቃለል የሚያደርጉትን ሩጫ መቃወም ብቻ ፋይዳ የሌለው መሆኑንን በተግባር እያየነው ነው። በጣም
ብዙ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ሆነው ጥሩ ያሬዳዊ መዝሙራትን መዘመር የሚችሉና ክፍተቱን መሙላት የሚችሉ ወጣቶችን በማኅበሩ መመሪያ መሠረት በግል መዝሙር ማሳተም አይፈቀድም በሚል አንድ ሞኝ ያሰረውን እንደተረቱ ሺዎች ሊፈቱት ባለመቻላቸው ይኽው ብዙ ከአለማዊ ዘፈን የተወሰዱ ዜማዎችና ሥጋዊ ነገር ላይ ብቻ ያተኮሩ መዝሙራዊ ዘፈኖች እስከ ቤተመቅደስ ድረስ ደርሰው ማንም ሊቆጣጠረው ከሚችለው በላይ ሆነዋል። በተቀደሰው ሥፍራ የረከሰው ነገር ቆሞ ሲያይ አንባቢው ያስተውል የሚለውም ትንቢት የተፈጸመ ይመስላል።

ከዘረዘርኩት የሚበልጡትን ትቼ ይህን የመጨረሻ እና በእኛ ትውልድ ስለተከሰተው ታላቅ የቤተክርስቲያን ፈተና ማኅበረ ቅዱሳን የያዘውን ፈጽሞ የተሳሳተ እና ከኃይማኖት፣ ከታሪክ እና ከእውነት ጋር የተቃረነ አቋም ባጭሩ ላንሳ።

አሁን ሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ስልጣን በያዘ ጊዜ ቀድሞ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤና በአብላጫ ድምጽ ለፕትርክና የተመረጡት 4ኛው ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ከስልጣናቸው ሲባረሩ የተፈጸመውን ነገር እውነቱን እና አሉባልታውን መርምሮና አውቆ የጠራ አቋም መያዝ ሲገባ ለእኛ ከተመቸን ስለሥርዓተ ቤተክርስቲያን የራሱ ጉዳይ በሚል የተፈጠረው ችግር እንዲባባስ የማኅበሩ ጭፍን አቋም ቤተክርስቲያንን ጎድቷል።

በጊዜው አሞኛል ብለው ለቀዋል የሚል ዜና በጋዜጣ ከመውጣቱ በስተቀር አሞኛል ሲሉ የተናገሩት ድምጽም ሆነ የጻፉት ደብዳቤ አልተሰማም አልታየም። ይህንንም ካሉ ወይንም ከፃፉ በኋላ እንደገና ልመለስ ሲሉ አንዴ ከለቀቁ አይቻልም ተብሎ ሌላ ተሾመበት የሚል ወሬ 23 አመት ይወራል። ከሁሉ የሚገርመው በቤተክርስቲያኗ ሕግ መንፈሳዊ ላይ አንድ ፓትርያርክ ከስልጣኑ የሚተካው ሲሞት ወይንም ለሞት የሚያበቃው ህመም ሲያጋጥመው ነው ይላል። ለሞት የማያበቃው ህመም ቢያጋጥመው ግን ከህመሙ እስኪፈወስ በቦታው አቃቢ ተሾሙ ከሕመሙ ሲፈወስ ሊመለስ ይችላል ልድገመው ሊመለስ ይችላል ነው የሚለው ሕጉ። የሚድን በሽታ የያዘው ስልጣን ከመያዝ ሊከለክል አይገባም ይላል። እኝህ አባት አሞኛል ብለው ለቀቁ ደሞ ልመለስ አሉ የሚለው ክስ እውነት እንኳን ቢሆን ከቤተክርስቲያኗ ሕግ አንጻር እርሳቸው ያደረጉትን አንዳች ስህተት አያሳይም። ለቀውም ከሆነ እንኳን ሊመለሱ መብት አላቸውና!

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ማኅበሩ በጭፍን ጠመንጃ ተገኑ ከሆነ ለጊዜው በሥጋ ሃይለኛ መስሎ ከታየው ጋር መቆሙና ቢያንስ የሆነው ሆኗል ከዚህ በኋል እንኳን እርቅና ሰላም ይውረድ አለማለቱ ነው። እንዲያውም በዚህ ዙሪያ በሚደረጉ የማጥላላትና በወደቀ ዛፍ ላይ ምሳር የማብዛት ድርጊት በቀጥታ ሲሳተፍ
በተደጋጋሚ ተስተውሏል። የመጀመሪያው ጥፋት ሳያንስም ለሁለኛ ጊዜ ይህ ጥፋት ሲደገም እርቅና ሰላም ይቅደም ከማለት ይልቅ ማኅበሩ አስመራጭ ኮሚቴ ውስጥ ገብቶ ተሳታፊ መሆኑ ማሞ ሌላ መታወቂያው ሌላ የሚያሰኘው ነው። ስለቤተክርስቲያን አንድነት እድገትና ሰላም የሚገደው ማኅበር መጀመሪያ በጭፍን አይወግንም። ኋላም እርቅና ሰላም እንዲመጣ የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል እንጂ ያወጣው ያውጣው አይልም። ለጊዜው ጨረስኩ። እግዚአብሔር በሰጠን ጊዜ ካልተማርን እርሱ ራሱ በጊዜ ያስተምረናል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!


የወቅቱ የኢትዮጵያ ወጣት እና ህወሓትን የማስወገድ ትግል

$
0
0

ታደሰ ብሩ

መግቢያ

አገራችን ኢትዮጵያ በሕዝብ ብዛት ከአፍሪቃ ሁለተኛ ስትሆን በተባበሩት መንግሥታት መመዘኛ “ወጣት” ተብሎ በሚጠራው የኅብረተሰብ ክፍል ብዛት ግን አንደኛ ነች። እርግጥ ነው ወጣነት በእድሜ ብቻ የሚገለጽ የኅብረተሰብ ክፍል አይደለም።  የሚከተለው የወጣት ትርጉም ሰፋ ያለ  ተቀባይነት ያለው ይመስለኛል።

0,,17657086_303,00

የኢትዮጵያዉያን ሰሚ ያጣ ጩኸት

ወጣት፣ በማኅበረሰቡ አንኳር ጉዳዮች ላይ እየወሰነ ባለው “አዋቂ” ተብሎ  በሚጠራው የኅብረሰተሰብ ክፍል እና ማኅበራዊ ፋይዳ ያላቸውን ውሳኔዎች ለመስጠት ገና ባልተዘጋጀው ሕፃን መካከል ያለ የኅበረተሰብ ክፍል ነው።

በዚህ ትርጓሜ መሠረት ወጣትነት የማኅበራዊ ግኑኝነት መገለጫ ጽንሰ ሀሳብ ነው። ይህ ማኅበራዊ ግኑኝነት ወደ እድሜ እንመዝረው ስንል ችግር ውስጥ እንገባለን፤ ምክንያቱም ወጣቱ ወደ አዋቂነት የሚሸጋገርበት ጊዜ እንደየአገሩ ባህሉና እንደ እድገቱ ይለያያል። በዚህም ምክንያት ነው የወጣትነት የህግ ትርጓሜዎች በየአገሩና ባህል የተለያዩ የሆኑት። ለምሳሌ፣ የተባበሩት መንግሥታት ወጣት ማለት “እድሜው 15 እስከ 24 ዓመታት ድረስ ያለው ሰው ነው” ሲል ይተረጉማል፤ ይሁን እንጂ የራሱ አካል የሆነው  UN Habitat “ወጣት ማለት እድሜው 15-32 ዓመት ያለው ሰው ነው” ይላል።  በአገሮች ትርጓሜ መካከል ያለው ልዩነት ደግሞ በጣም የተዘበራረቀ ነው። ዩጋንዳ ውስጥ እድሜው 12-30 የሆነ ዜጋ ወጣት ሲሰኝ ጎረቤትዋ ኬንያ ውስጥ 18-35 ነው። ስለዚህም አንድ የ16 ዓመት ወጣት ዩጋንዳዊ  ድንበር ተሻግሮ ኬኒያ ሲገባ ሕፃን ይሆናል፤ አንድ የ 32 ዓመት ኬንያዊ ወጣት ዩጋንዳ ሲሻገር ጎልማሳ ይሆናል።  ከአፍሪቃ ዝብርቅርቅ የወጣት ትርጓሜዎች ለአብነት ጥቂቶቹን ላንሳ: ሞውሪሸስ 14-29፣ ደቡብ አፍሪቃ 14-29፣ ናይጄሪያ 18-35፣ ጂቡቲ 16-30፣ ኬኒያ 18-35።

በ2004 ዓም የወጣው የኢትዮጵያ መንግሥት የወጣቶች ፓሊሲ ከ15 -29 ዓመታት ውስጥ የሚገኝን ኢትዮጵያዊን ዜጋን ወጣት ብሎ ይተረጉመዋል። በወጉ የሚያስተናግደው አላገኘም እንጂ ይህ ፓሊሲ በወጣበት ወቅት የኢትዮጵያ የወጣት ትርጓሜ እንደ ኬኒያና ናይጄሪያ 18- 35 መሆን ይገባዋል የሚል ሀሳብ ቀርቦ ነበር። የወጣቱ ከፓለቲካና ማኅበራዊ ውሳኔዎች መገለል መብዛትን በማጤን የላይኛው ጣራ እስከ 39 ከፍ ማለት አለበት የሚል ክርክርም ነበር። በበኩሌ ሥራአጥነትና ዘረኛ የህወሓት ፓሊሲ ያስፋፋው መድልዎና መገለል የወጣት የእድሜ ማዕቀፍ እንዲሰፋ አድርጓል ብዬ አምናለሁ። አርባ ዓመት አልፏቸው ከወላጆቻቸው ጥገኝነት ያልወጡ “ወጣቶች” ቁጥር በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ ነው። እኔ በዚህ አጭር ጽሁፍ ውስጥ ስለወጣት ስናገር እድሜው በ 18 እና 39 ዓመታት መካከል ያለውን ዜጋ እያሰብኩ ነው።

የዘመናችን ወጣት

0,,17014545_404,00የዘመናችንን ወጣት የሚተቹ በርካታ ጽሁፎች የወጡ ቢሆንም እኔ ብዙዎቹ ትችቶች አግባብ መስለው አይታዩኝም። በአንድ በኩል ወጣቱ የማኅበረሰቡ አካል በመሆኑ በወጣቱ ውስጥ የሚታየው ክፉም ሆነ ደግ ከማኅበረሰቡ የወረሰው ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ነገሮች ሁሉ ወጣቱ ላይ ይጎላሉ። በሌላው ዓለም ያለው የመብቶች መከበር እና የኑሮ ሁኔታ ከራሱ እውነታ ጋር ሲያመዛዝን የአንዳንዱ ወጣት ልብ በረሀ ለማቋረጥ፣ ባህር ለመሻገር እንዲደፍር ያደርገዋል፤ የአንዳንዱ ወጣት ልብ ደግሞ የማዕከላዊ እስር ቤትና በውስጡ ያለውን ቶርቸር እንዳይፈራ ያፀናዋል። የዘመናችን ወጣት ሊወደስባቸው የሚገቡ በርካታ ነጥቦች ቢኖሩም የሚከተሉት ግንባር ቀደም ናቸው ብዬ አምናለሁ።

 

  1. የዘመናችን ወጣት ማሰብ ተከልክሎ ያደገ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ማሰብና መመራመርን የሚያበረታቱ ሁኔታዎች የሉም ማለት ሁኔታዉን አቅሎ መመልከት ይሆናል። ምርምር የሚጀምረው ከመጠራጠር ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ግን ሥርዓቱ ትክክል ናቸው ያላቸውን ነገሮች መጠራጠር ወንጀል ነው። ኢትዮጵያዊ ወጣት “የምነግርህን ሳትጠራጠር አምነህ ተቀበል” ተብሎ ያደገ ነው። በዛሬቷ ኢትዮጵያ ውስጥ መረጃዎችን ማፈላለግ፣ ማንበብ፣ ማዳመጥ፣ ሀሳብ መለዋወጥ ወንጀል ነው። ወሳኝ በሆነ የፓለቲካና የፍልስፍና ጉዳዮች ላይ አቋም ይዞ መከራከር አይቻልም።  በከፍተኛ ትምህርት ተቋማትም የሚሰጠው ትምህርት እንደ ርዕዮተ ዓለም ቅስቀሳ ሁሉ “ያለቀለት እውነት” እንጂ ተማሪዎች በራሳቸው መንገድ ሊያረጋግጡት የሚገባ ጥሬ ሀሳብ ተደርጎ አይደለም። እንዲህ ዓይነቱ የአዕምሮ ውርጅብኝ የወረደበት ትውልድ ሆኖ እያለ ፈጽሞ  አለመደንዘዙ፤ ዛሬም በየእውቀት ዘርፉ ጎበዞች የሆኑ ወጣቶች መኖራቸው ድንቅ ነው። የዛሬ ወጣት አስተማሪም ትምህርት ቤትም ሳይኖረው – ያለ አስተማሪ እና ያለ ትምህርት ቤት – አሁን እደረሰበት ደረጃ ላይ መድረሱ ሊያስመሰግነው ይገባል።
  2. ከሰማንያ በመቶ በላይ የሆነው ወጣት ከኢህአዴግ ሌላ መንግሥት ኢትዮጵያ ውስጥ ኖሮ አያውቅም። እድሜውን በሙሉ ኢህአዴግ እና መንግሥት አንድ ሆነው ነው ያደገው። ስለአገራዊ አንድነት ከሰማው ስለ “ብሔር”፣ “ብሔረሰቦች” የሰማው በእጅጉ ይበልጣል። የአሁኑ ወጣት የኢትዮጵያ ታሪክ ተብሎ እየተነገረው ያለው የቂምና የበቀል ታሪኮችን ነው። አንድ የሃያ አምስት ዓመት ወጣት ዛሬ ያሉት ክልሎች ከጥንት ጀምሮ የነበሩ ቢመስሉት እንኳን ልንፈርድበት አይገባም። ከሬድዮና ከጋዜጣ ብቻ ሳይሆን ከወላጆቹ ጭምር ሲሰማው የኖረው ይህንኑ ነው። ዘረኝነት መንግሥታዊ ፓሊሲ በሆነበት፤ “አዋቂ” የሚባሉት ታላላቆቹ ራሳቸው ዘረኞች አሊያም በፍርሀት ተሸብበው ዝምተኞች በሆኑት አገር አድጎ ኢትዮጵያዊነትን ፈጽሞ አለመርሳቱ ይህንን ትውልድ በእጅጉ ያስመሰግነዋል።
  3. የዛሬ ወጣቶች በተለምዶ “ያ ትውልድ” የሚባለው ትውልድ ልጆች ናቸው። “ያ ትውልድ” ደግሞ ብዙ አልሞ የትም ያልደረሰ፤ ሊያጠፋው ከተነሳው አውሬ የባሰ ጭራቅ – ህወሓትን – ያነገሰ ነው። የዛሬ ወጣት ወላጆች በወጣትነታቸው የነቃ የፓለቲካ ተሳትፎ የነበራቸው ሊሆን ይችላል፤  ምናልባትም ማርክሲስትና ሌኒኒስቶች ሆነው ለላብ አደራዊ ወይም ወዛደራዊ ዓለም ዓቀፋዊነት ሲታገሉ ኖረው ይሆናል፤ አሊያም ነፃ አውጭዎች የነበሩ ሊሆኑ ይችላሉ። እርግጥ እነሱ በጽናትና ቆራጥነት ታግለው ሊሆን ይችላል። ያንን ስሜትና ጽናት ግን ወደ ወጣቱ አላስተላለፉትም። እንዲያውም “እኛም በጊዜዓችን ሞክረን አልቻልነውም” እያሉ የአዲሱን ትውልድ ሀሞት የሚያፈሱ ሆነዋል።  እንደ “ያ ትውልድ” ሁሉ ዛሬም እስርና ግርፋትን የማይፈሩ ወጣቶች መኖራቸው የሚያስመሰግናቸው ነው። እንደ “ያ ትውልድ” አየር ላይ ለተንሳፈፈ ርዕዮተ ዓለም ሳይሆን ለራሳቸውና ለሀገራቸው ክብርና ነፃነት ሕይወታቸውን ለመስጠት የቆረጡ ወጣት ወንዶችና ሴቶችን ስናይ ተስፋችን ይለመልማል። እርግጥ ነው እንዲህ ዓይነት ወጣቶች ቁጥራቸው ጥቂት ነው፤ የታሪክን ቦይ የሚቀዱት ግን እነዚህ ጥቂቶች መሆናቸው ጥርጥር የለውም።
  4. ስለዛሬው ወጣት ምግባረ ብሉሽነት ብዙ ይወራል። እኔ ይህ ትክክል አይመስለኝም። የሥራ አጥ ብዛት እንደ አሁን የተስፋፋበት ጊዜ የለም።  ዘጠና በመቶ ያህሉ ሥራ አጥ በወጣትነት የእድሜ ክልል ያለ ነው። “ትምህርቱን ጨርሶ” የሙሉ ጊዜ ሥራ አጥ ሆኖ የተቀመጠ ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ የከተማ ወጣት አለ። ሥራ አጥነት ከኢኮኖሚ ችግርነቱ የባሰው ማኅበራዊ ችግርነቱ ነው። ሥራ አጥ ሆኖ ኃላፊነት የሚሰማው እና በማኅበረሰቡ የሚደመጥ ዜጋ መሆን ከባድ ነው። ሥራ አጡን ወጣት ወደ አጓጉል ልማዶች የሚስቡት ክሮች ብዙ ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ ስናይ ግን ሁኔታው በሚወራው መጠን ተስፋ አስቆራጭ አይደለም። ዛሬም ሥጋ ቤቶች በሽቦ አጥር አልታጠሩም፤ ወርቅ ቤቶች አርቲፊሻል ሳይሆን እውነተኛ ወርቅ በመስታወት ውስጥ ዘርግተው ይሸጣሉ፤ ብዙ ምግብ ቤቶች ዋጋ ሳይቀበሉ ያስተናግዳሉ። እነዚህ ነገሮች ስናስተውል የኢትዮጵያዊውን ወጣት ሥነምግባር ማድነቅ ይገባናል ብዬ አስባለሁ።
  5. በከተሞች ተቀጥሮ የመሥራት እድል እየጠበበ ከመምጣቱ በላይ ያች ጠባብ እድልም በህወሓትና አጫፋሪዎቹ መዳፍ ውስጥ ናት። ህወሓት እና አጋፋሪዎቹ እያንዳንዱን የሥራ እድል “ሰው መግዣቸው” ሆኗል። በመንግሥት ሥራ ለመቀጠር ከትምህርትና ሙያ ይበልጥ የኢህአዴግ አባልነት ወሳኝ መሆኑ አገር ያወቀው ሀቅ ነው። ወጣቶች የራሳቸውን የግል ሥራ የሚፈጥሩበት ሁኔታም የለም። ነፃ አስተሳሰብ፣ ነፃ የንግድና የፍትህ ተቋማት በሌሉበት ስለ “ኢንተርፕሪነርሺፕ“ መስበክ ባዶ ዲስኩር ነው። በአንድ በኩል የወጣቱ የፈጠራ ተነሳሽነት እንዲላሽቅ ተደርጓል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ከመንግሥት ሥራ ያልተናነሰ የወያኔ ጥቃት በግሉ የሥራ ዘርፍ ውስጥም አለ። አፍቃሪ ወያኔ ያልሆኑ ነፃ ዜጎች የግል ቢዝነስ ቢጀምሩ እንኳ ሳንካዎች ይበዙባቸዋል፤ ሳንካዎችን ተቋቁመው አንገታቸውን ብቅ ካደረጉ በግብር እና በቫት ይኮረኩሟቸዋል፤ አቤቱታ ማሰሚያ ቦታ የለም።

በገጠር ያለውም ሀቅ ተመሳሳይ ነው።  የህወሓት የመሬት ፓሊሲ ግንባር ቀደም ሰለባ የሆነው የገጠር ወጣት ነው። መሬት ተሸንሽኖ አልቋል፤ ዛሬ ግማሽ ሄክታር መሬት ያለው ቤተሰብ ሀብታም ነው። በብዙ የአገራችን ክፍሎች ወጣት ገበሬዎች ከሩብ ሄክታር ያነሰ መሬት ይዘው ነው የራሳቸውን ትዳር የሚጀምሩት። ሩብ ሄክታር ለጓሮ አትክልት መትከያነት ቢሆን እንጂ ለሰብል አይበቃም። በአንፃሩ ደግሞ ግብርናንና ገበሬን የሚጠሉ “ኢንቬስተሮች” የሚይዙት መሬት የሚለካው በ10 ሺዎች ሄክታር ነው። ድሮ የማይታወቀው የገበሬ ሩቅ አገር መሰደድ አንዱ ምክንያት ይህ ነው። በገጠር ዘርን መሠረት ያደረጉ ግጭቶች ከሚያባብሱ ነገሮች አንዱ ይህ የመሬት እጥረት ነው።

በገጠርም በከተማውም ያለው ሀቅ ይህ ሆኖ እያለ ዛሬም አገሩን ከልቡ የሚወድ ወጣት መኖሩ የሚገርም ነው።

  1. አብዛኛው አዲስ ስደተኛ፣ ወጣት ነው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የኢትዮጵያ ስደተኛ ዓይነትና ስብጥር (demography) እና የስደተኛው  መዳረሻ አገሮች ተቀይረዋል። ወደ ደቡብ አፍሪቃ፣ ሱዳን እና አረብ አገሮች ያለው ስደት “ፍልሰት” በሚባል መጠን ነው። ወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች የማይታዩባቸው የገጠር መንደሮች ሞልተዋል፤ ወደ አረብ አገሮች አሊያም ደቡብ አፍሪቃና ሱዳን ነጉደዋል። አሜሪካ፣ አውሮፓና አውስትራሊያ የሚደርሰው ከስደተኛው ብዛት አንፃር ከቁጥር የማይገባው በጣም ትንሹ ነው። ታድያ በፓለቲካውም በኢኮኖሚውም ተደብድቦ፣ ተገፍቶ የወጣው ስደተኛ ወጣት ለአገሩ፣ ሕዝቡ፣ ባህሉና ታሪኩ ያለው ፍቅር የሚደንቅ ነው።
  2. የኢትዮጵያ ፓለቲካና ኢኮኖሚ አንድ መለያ ባህርይ “እጦት”  deprivation ነው። የፍትህ እጦት፣ የነፃነት እጦት፣ የመረጃ እጦት፣ የሚዛናዊ ትምህርት እጦት፣ የመሠረታዊ የጤና አገልግሎት እጦት፣ የመብራት ኃይል እጦት፣ የማገዶ እጦት፣ የመኖሪያ ቤት እጦት፣ የሥራ እድል እጦት፣ የኔት ዎርክ እጦት፣ የታክሲ እጦት፣ የእለት ጉርስ እጦት …. እጦት … እጦት  …  እጦት … ። ህወሓት እጦቶችን ተጠቅሞ ነው ወጣቱን እመዳፉ ውስጥ ለማስገባት እየጣረ ያለው።  (ህወሓት እና እጦት የረዥም ጊዜ ወዳጅነት እንዳላቸው የታወቀ  ነው፤ በድርቅ ለተጎዳው ሕዝብ በመጣ እርዳታ ራሱን ያደራጀ እጅግ ክፉና መሠሪ ድርጅት ነው) በእጦቶች የተጎዳ ሕዝብ ለእጦቶቹ ደረጃ ያወጣላቸዋል። መሠረታዊ እጦቶችን (ለምሳሌ የእለት ጉርስ፣ ኮንዶሚኒየም) ለማሟላት “ትላልቅ” እጦቶች (ለምሳሌ የፍትህና የመብት እጦቶችን) ይታገሳል።

0,,17658698_404,00አገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ ግን እጦቶችን በመሣሪያነት የሚጠቀም ፋሽስታዊ አገዛዝ ውስጥ አድገው እያለ ስለፍትህ፣ ስለነፃነት፣ ስለእኩልነት፣ ስለመብቶች የሚያሰላስሉ፣ የሚጽፉ፣ የሚታገሉ ብሩህ አዕምሮ ያላቸው ወጣቶች ያሉን መሆኑ መታደል ነው። ዛሬ ይህንን ማስታወሻ በምጽፍበት ወቅት በቃሊቲ፣ በቂሊንጦ፣ በዝዋይ እና በማይታወቁ በርካታ እስር ቤቶች ውስጥ በርካታ ወጣቶች ለፍትህ፣ ለሰብዓዊ ክብርና ነፃነት ዋጋ እየከፈሉ ነው።  እነሱን የመሰሉ በርካታ ወጣቶች ከእስር ቤቶች አጥሮች ውጭ በከተሞችም በገጠሮችም መኖራቸውን ሳስብ ደግሞ በዚህ ትውልድ ወጣቶች እኮራለሁ። ከዚህ አልፎ በእጦቶች መታሰር መሯቸው ወደ ተራራዎች ያቀኑ ወጣቶች መኖራቸው እና ቁጥራቸውም እያደር እየበዛ መሆኑ ስሰማ በዚህ ትውልድ ላይ መቅናት ያምረኛል።

  1. ኅብረት መፍጠር ቀላል የሚሆነው በቃላት ነው። “ተባበሩ” ብሎ መስበክ እና “እንዴት መተባበር አቃታችሁ” ብሎ መዝለፍ በጨለማ ሌሊት ወደ ሰማይ አንጋጦ ከዋክብትን የመቁጠር ያህል አዝናኝ ነው። መተባበር የትም አገር ቢሆን ከባድ ነው። እኛ አገር ደግሞ ይበልጥ ከባድ የሚያደርጉት ሁኔታዎች አሉ። (በነገራችን ላይ ህወሓት፣ ኢህአዴግ ላይ እንዳደረገው ዓይነት የአፈና ጥርነፋን “ኅብረት” ብለው የሚጠሩ ሰዎች አሉ) የመተባበር ችግራችን ዛሬ የተጀመረ አይደለም። መተባበር ያስቸገረን በፓለቲካው መስክ ብቻም አይደለም። ሌላው ቀርቶ ስለ ኅብረት ሲሰብኩ ውለው ሲሰብኩ የሚያድሩ የሃይማኖት አባቶችም እርስ በርሳቸው መተባበር አልቻሉም።

የመተባበር ችግር ለህወሓት ምቹ ሁኔታ ፈጥሮለታል፤ ልዩነቶችን እያራገበ፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ እየተሳለቀ ተዝናንቶ ይገዛል። ዉጣ ውረድ የበዛበት አስቸጋሪ መንገድ ቢሆንም እንኳን በዚህም ረገድ የተስፋ ጭላንጭል እየታየኝ ነው። ከሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ወጣቶች ወደ ፓለቲካ አመራር እየመጡ ነው። ከሰሜን፣ ከደቡብ፣ ከምሥራቅ፣ ከምዕራብና ከመሀል አገር የተወጣጡ ወጣቶች ለጋራ ኢትዮጵያ ሲሰለፉ፤ ያንንም ትግል በጋራ ሲመሩ ማየት የሚያኮራ ነው። የተለያዩ እምነቶች ተከታዮች የሆኑ ወጣቶች በፓለቲካ ድርጅት አመራርነት ተመርጠው በጋራ ሲሰሩ ማየት ተስፋ ሰጪ ነው። ለአንድ የጋራ ዓላማ ጉልበትን በማስተባበር ረገድ ብዙ ይቀረናል፤ ተግዳሮቶቹ በርካታ ናቸው፤ ያም ሆኖ ግን በወጣቱ በኩል እየታየው ያለው መናበብ ተስፋ ሰጭ ነው። የዛሬ ወጣት ውብ ኢትዮጵያን ከምናቦቻችን አውጥቶ በእውን ሊፈጥራት የታደለ ትውልድ ነው፤ ይህን ለማድረግ ደግሞ ብቃት አለው ብዬ አምናለሁ።

ቁጭት

ከላይ የዘረዘርኳቸው ስምንት መልካም ነገሮችን አዳብረናቸው፤ የወጣቱን ጉልበትና ተነሳሽነት በሚገባ ተጠቅመንበት ቢሆን ኖሮ እስካሁን የት በደረስን?

እነዚህን ስምንት አበረታች ነገሮች በሚገባ አሳድገናቸው ቢሆን ኖሮ:

  • ሰዎች ለመናገር፣ ለማንበብ፣ ለመስማት፣ ለመፃፍ የሚሸማቀቁበት አገር ዜጎች ባልሆንም ነበር፣
  • በራስ መተማመንን ያዳበሩ በርካታ ድንቅ የተፈጥሮና የማኅበራዊ ሳይንስ ባለሙያዎች፣ የፈጠራ ሰዎች በሕዝብ የተወደዱ ወጣት መሪዎች፣ በጥረታቸው የተሳካላቸው የቢዝነስ ሰዎች፣ … ወዘተ በኖሩን ነበር፣
  • ትምህርት፣ አዕምሮን ማደንቆሪያ መሆኑ ቀርቶ የምርምን አድማስን ማስፊያ፣ አዕምሮን ማበልፀጊያ እና ሙያ መቅሰሚያ ይሆን ነበር፣
  • ኢትዮጵያችን እንደአሁን የተማረው የሚሸሻት ሳይሆን የወጣው የሚመለስባት አገር ትሆን ነበር፣
  • የኢትዮጵያ ሕዝብ የህወሓት መጫወቻ፤ የአገሪቱ ሀብት ደግሞ የሹማምንቱ መድለቢያ ባልሆነ ነበር፣
  • የዘር ፓለቲካ መንግሥታዊ ፓሊሲ ሆኖ እርስ በርሳችን መግባባት እስከሚያቅተን ድረስ ለራሳችን ወንድሞችና እህቶች ባዕዶች ባልሆንም ነበር፣
  • ገበሬው ከማሳው ባልተፈናቀለ፤ በድህነት፣ በስደተኛና በእስረኛ ብዛት ብዛት ዓለምን መምራታችን ይቀርልን ነበር፣
  • በሀገራችንም በውጭ አገራትም ወጣቶቻችን አንገታቸውን ቀና፣ ደረታቸውን ነፋ አድርገው በሄዱ ነበር፤  እህቶቻችን በአረብ ጎረምሶች ከሚደርስባቸው ስቃይ በተገላገሉ ነበር፣
  • አገሪቱን የሚመሯት እኛው ፈልገንና ፈቅደን የመረጥናቸው፤ ካልተስማሙን የምንሽራቸው፤ የምናከብራቸው እንጂ የማንፈራቸው፤ በፓሊስና በወታደር የማያስደበድቡን “የኛ” የምንላቸው ሰዎች በሆኑ ነበር፣
  • ሌሎችም ብዙ መልካም ነገሮችን ባየን ነበር፣

ምልከታ

ባለፈው መቆጨት መልካም የሚሆነው ለወደፊቱ ምልከታ ሲያገለግል ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ አዎንታዊ ለውጥ በፍጥነት እንዲመጣ የወጣቱ ተሳትፎ አሁን ካለበት በጣም መጨመር ይኖርበታል። ይህን ማድረግ ደግሞ ይቻላል፤ ወጣቱ፣ አቅም፣ ችሎታውና ተነሳሽነቱ አለው። ወጣቱ በራሱና በአገሩ የወደፊት እጣ ፈንታ ላይ አዎንታዊ ሚና  እንዲኖረው በራሱ ላይ ያለውን መተማመን ማዳበር ይኖርበታል፤ አፈናን በሚሰብር መልኩ ራሱን ማደራጀት ይጠበቅበታል። እንዲህ በተጠና መንገድ የሚንቀሳቀስ ከሆነ ትናንንሽ የሚመስሉ ጥረቶች ተብላልተው ትልቅ ሕዝባዊ ማዕበልን መፍጠር ይችላሉ።  ይህንን ትግል አሁን በኢትዮጵያ ፓለቲካ ውስጥ በተለያዩ ስልቶች በሚንቀሳቀሱ የፓለቲካ ድርጅቶች ውስጥ በአመራር ጭምር በመሳተፍ ሊደረግ ይችላል። ይህ በማይመችበት ጊዜ ደግሞ የተለያዩ የአደረጃጀት ስልቶችን መጠቀም ይገባል።

የኢትዮጵያ ወጣት ሁሉ አንድ ዓይነት አመለካከት ወይም የተቀራረበ አመለካከት ይኖረዋል የሚል ብዥታ የለብኝም። ሆኖም ግን ከዚህ በታች ያለው ጽሁፍ የሚያተኩረው ተስፋው በህወሓት የተነጠቀው አብዛኛውን ወጣት እያሰብኩ ነው።

የኢትዮጵያ ወጣትን ትግል ለማገዝ ሶስቱ የመዳረሻ (tipping point) ህግጋትን በሚገባ መረዳት እና በሥራ ላይ ማዋል ይጠቅማል ብዬ አምናለሁ። ሶስቱ የመዳረሻዎች ህግጋት (1) የአናሳዎች ህግ  (Law of the Few)፣  (2) መጣበቅ (Stickiness Factor) እና (3) የሁኔታዎች ህግ (The Law of Context) ናቸው።

  1. የአናሳዎች ህግ፣ በሚገባ የተደራጁ ጥቂት ሰዎች ትልቅ ሕዝባዊ ማዕበልን ማስነሳት ይችላሉ የሚለው መርህ ነው። ይህ በማኔጅመንት ውስጥ “መርህ 80/20” (The 80/20 Principle) ከሚባለው ጋር ይዛመዳል። ለምሳሌ በ 20% ጥረት 80% ውጤት እንደሚገኘው ማለት ነው። በአንድ የሥራ ቦታ 100 ሠራተኞች ቢኖሩ አብዛኛውን ጊዜ 80% ያህሉ የሥራ ሸክምና ኃላፊነት የሚወድቀው ከ 20 ባልበለጡ ሠራተኞች ላይ ነው። እነዚህ 20 ለይቶ ማወቅ፣ መሸለም፣ ማሰልጠንና ማበረታታት የጥሩ ማኔጀር ሥራ ነው። በማኅበራዊ ንቅናቄዎችም እንደዚሁ ነው። ጥቂቶች ናቸው ወሳኙን ሥራ የሚሰሩት – ወሳኝ ጥቂት ሰዎች (the vital few).

 

ከእነዚህ ጥቂት ሰዎች መካከል በወጣቱና በማኅበረሰቡ ተሰሚነት ያገኙ፤ ሲናገሩ የሚደመጡ፤ ንቅናቄውን ወደ በጎ ነገር ይመሩታል ብለው ተከታዮቻቸው እምነት የሚጥሉባቸው “አውራዎች”  ወይም የኔታዎች (Mavens) ያስፈልጋሉ። በእድሜ ከወጣትነት የዘለሉ ዜጎች አንዱ ገንቢ ሚና ይህንን ቦታ መሙላት ነው። ሌላው እጅግ አስፈላጊ ነገር የግኑኝነት መረብ (Network) መዘርጋት ነው። እያንዳንዱ የትግሉ ተሳታፊ ከበርካታ ሰዎች ጋር በመገናኘት አድማሱን ማስፋት ይገባል። ግኑኝነት ለመፍጠር ወጣቱ የሚወዳቸውንና የሚያዘወትርባቸው መስኮች ማወቅና አክብሮት ለሚገባቸው አክብሮት መስጠት ያስፈልጋል። ስፓርት፣ ኪነ ጥበብ፣ የእምነት ተቋማት፣ ት/ቤቶች …  ሊዳሰሱ ይገባል። አንዳንድ ወጣቶች በተፈጥሮዓቸው ብዙ ኔትዎርክ አላቸው። እንዲህ ዓይነቶቹን ወጣቶች የንቅናቄው አካል ማድረግ በጣም ጠቃሚ ነው፤ ያለ ብዙ ድካም ወጣቱን የማገናኘቱን ሥራ ያቀላጥፉታል። በሶስተኛ ደረጃ ደግሞ የቀስቃሾች መኖር እጅግ አስፈላጊ ነው። ቀስቃሾች ንግግርን፣ ሙዚቃን፣ ስዕልን … ወዘተ በመጠቀም ቁጥሩ እጅግ በርካታ የሆነ ሕዝብን በአንድ መስመር ውስጥ ማስገባት ዋነኛው ሥራቸው መሆን ይኖርበታል።

 

“መሰብሰብ ወንጀል በሆነበት አገር እነዚህ ‘ጥቂቶች’ እንዴት ይገናኛሉ? እንዴትስ ይደራጃሉ?” የሚል ጥያቄ እንደሚነሳ እገምታለሁ። ስለወጣት ድርጅቶች ስናስብ በሃሳባችን መምጣት ያለባቸው አባላትን መዝግበው፣ መዋቅር አዘጋጅተው ተመዝግበውም ሆነ ሳይመዘገቡ የሚሠሩ መደበኛ ድርጅቶችን ብቻ አይደለም። አፈና በበዛበት ሥርዓት ውስጥ ኢመደበኛ ድርጅቶች (informal organisations) ከመደበኛዎቹ የተሻለ ሊያገለግሉ ይችላሉ። የስፓርት ቡድን ደጋፊዎች፣ የመፃህፍት አፍቃሪያን ስብስቦች፣ የአገርህን እወቅ ክበባት፣ የአካባቢ ጥበቃ ማኅበራት፣ የቴኳንዶና ማርሻል አርት ክበባት፣ የሙዚቃ ክበባት፣ የማርያም፣ የሥላሴ፣ የገብሬል … ጽዋ ማኅበራት፣ ደብተሮች፣ እርሳስና እስክሪብቶዎችን ለድሆች ተማሪዎች አሰባሳቢ ክበባት፣ በረንዳ አዳሪዎችን አልባሽ ማኅበራት፣ እቁቦችና ትናንሽ እድሮች እና የመሳሰሉት ሁሉ የመደበኛ የወጣት ድርጅት ምትክ ሆነው ሊያገለግሉ ይችላሉ።

 

  1. መጣበቅ (Stickiness Factor)፤ ይህ ህግ የመልዕክቱ ይዘትና አቀራረብን የሚመለከት ነው። መልዕክቱ በቀላሉ መዳረስ ብቻ ሳይሆን ከተቀባዩ ጋር “መጣበቅ”  አለበት።  መልዕክት በብዛት ቢዳረስም ሆነ በተከበሩ ሰዎች አንደበት ቢነገርም እንኳን አድማጩ አዕምሮ ውስጥ የማይቀር ከሆነ ማዕበል የማስነሳት አቅም አይኖረውም። የመልዕክቱ ይዘት ደግሞ ቀላልና ግልጽ ብቻ ሳይሆን ወደሌሎች  ለማዳረስም የሚያጓጓ መሆን ይኖርበታል።

 

ወጣቱ የትግሉን ግብ በግልጽ ቢያስቀምጥ ይጠቅማል ባይ ነኝ። መልዕክቶች አጭርና ቀላል ሆነው ወደ ተግባር የሚመሩ መሆን ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ የወጣቱ እንቅስቃሴ ዓላማ በሚከተለው አኳኋን በአጭሩ ማቅረብ ይቻላል።

 

ህወሓት በሕዝባዊ እምቢተኝነትና አመጽ ይወገዳል፤ ሰፊ ውክልና ያለው የሽግግር መንግሥት ይመሠረታል። የዜጎች፣ የሃይማኖቶች፣ የብሄር/ብሄረሰቦች፣ የቋንቋዎች እኩልነት ይከበራል፤ ገለልተኛ ተቋማት ተመሥርተው በሁሉም እርከኖች የመንግሥት ሥልጣን በነፃ የሕዝብ ምርጫ ይወሰናል። አዲሱ ሥርዓት ለሁላችንም የሚበጅ ስለሆነ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጎናችን ይቁም። በተለይ የመከላከያ ሠራዊትና ፓሊስ ከሕዝብ ጋር ወግኑ፤ የኢህአዴግ አባላትም በሕዝብ ጎን በመቆም ታሪክ ስሩ።

 

መልዕክቶችን በምስል፣ በተረት፣ በምሳሌ፣ በቀልድ ወዘተ ማስተላለፍ መለመድ ይኖርበታል። !!

 

  1. የሁኔታዎች ህግ (The Law of Context)፤ አካባቢያዊ ሁኔታዎች በእንቅስቃሴዎቻችን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ  እንዳላቸው ማመን ተገቢ ነው። የትግል ስትራቴጂና ስልት በአብዛኛው የሚወሰኑት በሁኔታዎች ነው። እኛ በሁኔታዎች ላይ ሙሉ ቁጥጥር የለንም። በዚህም ምክንያት ከአንድ ዓይነት የትግል ስልት ጋር “መቁረብ” በጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል። ወጣት መሪዎች ሁኔታዎችን እያጠኑ ተስማሚ ስትራቴጂዎችንና ስልቶችን መቀየስ መልመድ ይኖርባቸዋል። በአንዱ ቦታ የሠራው በሌላ ቦታ ላይሰራ እንደሚችል፤ የነጠረ፣ ብቸኛ የሚባል ስትራቴጂ እንደሌለ መገንዘብ ይጠቅማል።

 

አጣዳፊ ሥራዎች

ሁሉንም  ሥራዎች በአንድ ጊዜ  መፈፀም የማንችል በመሆኑ  ቅደም ተከተል ማውጣት ግድ ነው። በኔ ግምት አሁን የለውጥ ዋዜማ ውስጥ እንገኛለን። በዚህ ወቅት በስፋት መሠራት ያለባቸው ሁለት ነገሮች ወጣቶችን ማንቃትና ለለውጥ ማዘጋጀት እና ኔትዎርኮችን ማስፋት ናቸው። በሌላ አነጋገር መቀስቀስ እና ማደራጀት የወቅቱ ሁለት አጣዳፊ ሥራዎች ናቸው።

 

ወጣቱን ለመቅስቀስ ያሉት የመቀስቀሻ መሣሪያዎችን ሁሉ – ቴሌቪዥን፣ ሬድቶ፣ ጋዜጣ፣ ማኅበራዊ ሚዲያዎች፣ በራሪ ጽሁፎች፣ ስብሰባዎች፣ የሰው ከሰው ንግግሮች እና ሌሎችም መንገዶች ሁሉ መጠቀም አለብን። ለማደራጀት ደግሞ  ከላይ እንደተገለፀው መደበኛ ድርጅቶችን ብቻ ሳይሆን ኢመደበኛ ድርጅቶችን መጠቀም መልመድ አለብን።

 

ከኢትዮጵያ ወጣት 10% እንኳን በዚህ ሁኔታ ቢዘጋጅ የህወሓት አገዛዝ ሊሰነብት አይችልም፤ ይህ ደግሞ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊፈፀም የሚችል ነው።

ለአስተያየት tkersmo@gmail.com

***

 

ትላንት «መብራት የለም» በሚል ምክንያት ያልተካሄደው የውድ ኮሜቴዎቻችን ችሎት ዛሬ ተሰይሞ ውሏል!

$
0
0

የታሪክ ምሁሩ አህመዲን ጀበል አስደናቂ ምስክርነቱን ሰጥቷል!

ማክሰኞ ህዳር 23/2007

10428563_863640397020651_48239593080031941_nበትላንትናው ዕለት አቃቤያነ ህግጋት፣ የውድ ኮሚቴዎቻችን ጠበቆችና ዳኞች ተገኝተው የነበረ ቢሆንም እንደተለመደው ‹‹መብራት የለም›› በሚል ምክንያት ሳይካሄድ የዋለው የውድ ኮሚቴዎቻችን የችሎት ሂደት በዛሬው እለት ቀጥሎ ዋለ! የዛሬው ችሎት ኮሚቴዎቻችን እርስ በእርስ ምስክርነት የሚያሰሙበት ሂደት አካል የነበረ ሲሆን ለዛሬ የመከላከያ ምስክርነቱን ያስደመጠውም የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴው አባልና የታሪክ ምሁሩ፣ እንዲሁም የክስ መዝገቡ ሁለተኛ ተከሳሽ የሆነው አህመዲን ጀበል ነበር፡፡ የመሰከረውም ለመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴው ጸሐፊ ኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋ ነበር፡፡

አህመዲን ጀበል በምስክርነቱ የማእከላዊ መርማሪዎች ለእስልምና ሃይማኖት ያላቸውን ንቀት በተደጋጋሚ ያንጸባረቁ መሆናቸውን የገለጸ ሲሆን ኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋ በምርመራ ወቅት ሶላት ደርሶበት አስፈቅዶ ሲሰግድ መርማሪዎቹ በሚሰግድበት ቦታ ጫማቸውን ወደራሱ በማስጠጋት ‹‹በፊት ለአላህ ነበር የምትሰግደው፤ አሁን ለእኛ ነው የምትሰግደው›› ብለው እስከመሳለቅ የደረሰ ድፍረትና ወንጀል የፈጸሙ መሆናቸውን አጋልጧል፡፡ ኡስታዝ አህመድ በስግደት (ሱጁድ) ላይ እንዳለ ጀርባው ላይ ይቆሙበት እንደነበር በመግለጽም መርማሪዎቹ በህገ መንግስት ጥበቃ ለተሰጠው ሃይማኖታዊ መብት ምን ያክል ንቀት እንደነበራቸው ያሳዩበትን አጋጣሚ ዝርዝሮ አስረድቷል፡፡

ከኡስታዝ አህመድ ጋር ከ2000 ጀምሮ ይተዋወቁ እንደነበር የጠቀሰው አህመዲን ጀበል በማዕከላዊ እስር ቤት በተለምዶ ሳይቤሪያ ተብሎ በሚጠራው ክፍል ውስጥ አብረው ታስረው እንደነበርና ከምርመራ መልስ ኡስታዝ አህመድ ፊቱ ተጋግጦ፣ ዝሎ እና ተዳክሞ ይመጣ እንደነበር ገልጿል፡፡ በሃምሌ 5 ምሽትም ለምርመራ ወስደውት ከፍተኛ ኢ-ሰብዓዊ ድብደባ ያደረሱበት መሆኑን፣ እግሮቹ በደም እስኪታጠቡ ድረስ ውስጥ እግሩን መደብደቡን፣ ልብሱ ላዩ ላይ በደም እስኪጣበቅ መድረሱንና በብረት ዱላ ጣቶቹ እንደተደበደቡ ዘርዝሮ አስረድቷል፡፡ ከሌሊቱ 9 ሰዓት አካባቢ እንደመለሱትና በምርመራ ወቅትም ይህንን መሰል ድብደባዎች በተደጋጋሚ እንደተፈጸሙበት ለፍርድ ቤቱ ገልጿል።

በምስክር ማስደመጡ ሂደት ከኮሚቴው ጠበቆች በኩል ‹‹አህመድ ሙስጠፋ የተደበደበበት ምልክት አሁንም ድረስ ጠባሳው ስላለ ፍርድ ቤቱ ይህንን በተጨባጭ እንዲያየው እግሩ በችሎቱ ፊት ይታይ›› የሚል ጥያቄ በመቅረቡ ምክንያት አንድ ፖሊስ ከችሎቱ ውጪ የተከሳሹን እግር አይቶ የተመለከተውን እንዲገልፅ የታዘዘ ሲሆን ፖሊሱም በኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋ እግር ላይ ጠባሳ ማየቱን ለፍርድ ቤቱ አሳውቋል።

ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

ለንግዱ ማህበረሰብ የቀረበ ጥሪ –ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር

$
0
0

negere-ethiopia-photo1የንግድ ማህበረሰብ ለአንድ አገር ምሰሶ ነው፡፡ በዴሞክራሲ በበለጸጉ አገራት የንግዱ ማህበረሰብ ለራሱ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ብቻ ሳይሆን ያለውን ፈርጣማ የኢኮኖሚያዊ አቅምና ኢኮኖሚያዊ አቅሙ የሚፈጥርለትን የተሻለ ንቃተ ህሊና በመጠቀም ለጭቁኖች መከታ ሲሆን ታይቷል፡፡ ለዚህም ነው የንግዱ ማህበረሰብ ዴሞክራሲን በመገንባት ትልቅ ሚና እንዳለው የሚነገርለት፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ እስካሁን ባለው ሁኔታ የንግዱ ማህበረሰብ በነጻነት ሰርቶ የሚበለጽግበት፣ ወገኑንና አገሩን በተለያየ መንገድ የሚያግዝበት መንገድ በመዘጋቱ የሚገባውን ያህል አስተዋጽኦ አበርክቷል ለማለት ይከብዳል፡፡

ኢህአዴግ ወደ ስልጣን በመጣበት ጊዜ ነጻ ገበያን እንደሚከተል በመግለጹ የንግዱ ማህበረሰብ በነጻ ገበያ መርህ ተወዳድሮ ራሱንም አገሩንም ይጠቅማል የሚል ተስፋ የነበረ ቢሆንም ይህ ተስፋ እውን ሳይሆን ቀርቷል፡፡ ይልቁንም ገዥው ፓርቲ የራሱን የኢኮኖሚ ኢምፓየር በመመስረት የአገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ስርዓት አበላሽቶታል፡፡ በራሳቸው ነግደው የሚያድሩ ኢትዮጵያውያን መካከል ግልጽነት በጎደለው መንገድ የአገሪቱን አንጡራ ሀብት እየተጠቀሙ ከሚገኙት የገዥው ፓርቲ ግዙፍ ኩባንያዎች ጋር መወዳደር አቅቷቸው የከሰሩት በርካቶች ናቸው፡፡ በተለያየ መንገድ አሁንም ድረስ የቀጠሉትም ቢሆን ከገዥው ፓርቲ ተቋማት ጋር መወዳደር ተስኗቸው ለራሳቸውም ሆነ ለአገራቸው ማበርከት የነበረባቸውን አስተዋጽኦ እንዳያበረክቱ ተደርገዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ለገዥው ፓርቲ ባለማደራቸው ምክንያት አግባብ ያልሆነ ቀረጥና ሌሎች ጫናዎች እየተጣሉባቸው አንድም ከገበያ ወጥተዋል፡፡ አሊያም የሚገባቸውን ጥቅም ማግኘትና አገራቸውን መጥቀስ ሳይችሉ ቀርተዋል፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ለገዥው ፓርቲ መዋጮ እንዲከፍሉ ከመጠየቃቸውም በላይ ስርዓቱ ባነገሰው ሙስና ምክንያት እጅ ተወርች ተይዘው ራሳቸውን፣ ህዝባቸውንና ለአገራችን ዴሞክራሲ ግንባታ ያበረክቱትን የነበረው አስተዋጽኦም ተገድቧል፡፡
በሌላ በኩል በገበያው ላይ የሚቆየው ለስርዓቱ ያደረ ብቻ በመሆኑ በርካቶች ለአገር ከመስራት ይልቅ ለገዥው ፓርቲ ማደር መርጠዋል፡፡ በዚህም አንድ የንግድ ማህበረሰብ ለአገሩ ያበረክት የነበረውን አስተዋጽኦ ረስተው የተሳሳተ መንገድ ይዘዋል ብለን እናምናለን፡፡ ራሳቸውን ለገዥው ፓርቲ አሳልፈው በመስጠታቸውም ታሪካዊ ግዴታቸውን ሳይወጡ ቀርተዋል፡፡ ይህን ስንል ግን ከገዥው ፓርቲ ተጠግተው ከሚያገኙት ጥቅም ይልቅ ከህዝብ ጋር ቆመውና ግዴታቸውን እየተወጡ መስዋዕትነት የሚከፍሉ የሉም ማለት አይደለም፡፡ ሆኖም በአሁኑ ወቅት የንግዱ ማህበረሰብ የሚጠበቅበትን ያህል እየሰራ እንዳልሆነ ለመጠቆም እንወዳለን፡፡

የንግዱ ማህበረሰብ ስርዓቱ በራሱም ሆነ በአገሩ ላይ የሚፈጽመውን ህገወጥነት በየግሉ ከመቃወምም ባሻገር ትግሉን በማገዙ ወደፊት ለራሱም ሆነ ለአገሩ የሚያሰራ ስርዓት መፍጠር ይችላል ብለን እናምናለን፡፡ በመሆኑም ስርዓቱ በራሱና በአገራችን ላይ የሚፈጽመውን በደል በመቃወም ላይ የሚገኙትን ተቃዋሚዎች ትግል በሞራል፣ በገንዘብና በሌሎችም ድጋፎች በማገዝና ትግሉን በመቀላቀል ለንግዱ ማህበረሰብና ለኢትዮጵያ የሚያዋጣትን ስርዓት እንድንመሰርት ጥሪ እናደርጋለን፡፡

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ለንግዱ ማህበረሰብና በአጠቃላይም ለኢትዮጵያ የሚመች ስርዓት ለመፍጠር በጋራ እየሰራ ይገኛል፡፡ ከዚህም መካከል ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል መርሃ ግብር ቀርጾ በመንቀሳቀስ ላይ ሲሆን ህዳር 27/28 2007 ዓ.ም የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ያደርጋል፡፡ ይህ ሰላማዊ ሰልፍ ኢትዮጵያውያን መብታቸው ተከብሮ የሚኖሩባት ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመፍጠር ጮራ የሚፈነጥቅ ነው ብለን እናምናለን፡፡ በመሆኑም የራሱንም መብት በማስከበርና የአገሩን ዴሞክራሲ በመገንባት ታሪካዊ ሚና ያለው የንግዱ ማህበረሰብ ትግላችን በመቀላቀል፣ በገንዘብና በሞራል በመደገፍ የዚህ ታሪካዊ ትግል አካል እንዲሆን ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ያለ መስዋዕትነት ድል የለም!

ታሪካዊ ግዴታችን በመወጣት ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንገንባ!

ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር በመተባበር የባቡር አካዳሚ ልትገነባ ነው

$
0
0

የኢትዮጵያ መንግሥት ከቻይና ጋር በመተባበር በአፍሪካ ቀዳሚ የሚሆን የባቡር አካዳሚ በአዲስ አበባ ለመገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑን ገለጸ፡፡ በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪና የኢትዮጵያ ባቡር ኮርፖሬሽን ቦርድ

f4dd5c1a7bbb150619bc2bac1c3d9648_Lሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር አርከበ እቁባይ ባለፈው ማክሰኞ የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ የተመረጡ ኩባንያዎች ስምምነት ሲፈርሙ በተገኙበት ወቅት ነው የመንግሥትን ዕቅድ ይፋ ያደረጉት፡፡

ከፊርማው ሥነ ሥርዓቱ በኋላ ሪፖርተር ስለአካዳሚው ያነጋገራቸው ሲሆን፣ አካዳሚውን የመገንባት ሥራ ሙሉ በሙሉ በዚህ ዓመት እንደሚጀመር ገልጸዋል፡፡

በእስካሁኑ ጥረት ማዕከሉን የመገንባትና የመምራት ኃላፊነት የሚኖረውን ኩባንያ ለመምረጥ ዓለም አቀፍ ጨረታ እንደወጣና ሦስት የቻይና ኩባንያዎች ተመርጠው ግምገማ እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

አካዳሚው በባቡር ትራንስፖርትና መሠረተ ልማት ግንባታ ከአስተዳደር ጀምሮ፣ በኢንጂነሪንግ፣ በኦፕሬሽን፣ በጥገናና በመሳሰሉት ሁሉን አቀፍ ሥልጠና የሚሰጥ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡

ከተመረጡት ኩባንያዎች ብቃት ያለው አንዱን የመለየት ሥራ በሚቀጥለው ወር መጨረሻ ድረስ ይታወቃል ያሉት ዶ/ር አርከበ፣ የሚመረጠው ኩባንያ ማዕከሉን ከመገንባትና ከማደራጀት በተጨማሪ ማዕከሉን የሚመሩና አሠልጣኝ መምህራንን ይዞ የመጀመሪያዎቹን ጥቂት ዓመታት አካዳሚውን ያስተዳድራል ብለዋል፡፡

‹‹ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ከቻይኖቹ ጋር በመሆን ልምድ ይወስዳሉ፡፡ ከተወሰነ ዓመት በኋላ ምናልባትም ከአምስት ዓመት በኋላ አካዳሚውን ሙሉ በሙሉ ኢትዮጵያውያን ይመሩታል፤›› ብለዋል፡፡

አካዳሚው ሲቋቋም ጀምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታይና አቅም የሚፈጥር እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግሥት ፍላጐት መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር አርከበ፣ የዚህ ምክንያትም አካዳሚው የሰው ኃይል የሚያፈራው ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ አገሮችም ምርጫቸው የሚያደርጉት እንዲሆን ነው ብለዋል፡፡ ይህ መሆን እንደሚችል ደግሞ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የአቪዬሽን አካዳሚ ስኬት ልምድ መውሰድ ይቻላል ብለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ሥር ያለው የሰው ኃይል ዘጠና በመቶ ለባቡር ትራንስፖርትና መሠረተ ልማት ዝርጋታ አዲሶች በመሆናቸው፣ መንግሥት ክፍተቱን ለመሙላት ከ250 በላይ ወጣት ኢንጂነሮችንና ቴክኒሺያኖችን በመመልመል በቻይናና በሩሲያ አገር እያሠለጠነ ይገኛል፡፡ በዚህም ምክንያት በዓመቱ መጨረሻ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ የሚጠበቀውን የአዲስ አበባ ቀላል የባቡር ፕሮጀክት ትራንስፖርትና ጥገና ሁለት የቻይና ኩባንያዎች የፈጠሩት ጥምረት እንዲመሩት ተደርጓል፡፡

ሁለቱ ኩባንያዎች በቻይናዋ ሸንዘን ከተማ የባቡር ትራንስፖርት የሚሰጠው ሸንዘን ሜትሮ ግሩፕና የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ግንባታን የሚያከናውነው ቻይና ሬልዌይ ኢንጂነሪንግ (CREC) ናቸው፡፡

ሁለቱ ኩባንያዎች በቻይና መንግሥት ባለቤትነት የሚተዳደሩ ሲሆን፣ የሁለቱም ኩባንያዎች የቦርድ ሊቀመንበሮች በተገኙበት እንዲሁም በኢትዮጵያ በኩል ዶ/ር አርከበና ሌሎች የቦርድ አባላት ባሉበት የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ስምምነቱን ከሁለቱ ኩባንያዎች ጋር ፈርመዋል፡፡

የሁለቱ ኩባንያዎች ጥምረት የባቡር ትራንስፖርትና ጥገናውን ለአምስት ዓመት የሚያከናውኑ ሲሆን፣ በቆይታቸውም 116 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡

ኩባንያዎቹ አገልግሎቱን ለመስጠት የሚያሳትፏቸው ሠራተኞች ብዛት 686 እንደሚሆን ሪፖርተር በቅርቡ መዘገቡ ይታወሳል፡፡ በመጀመሪያው ዓመት ውስጥ 290 ቻይናውያንና 52 በመቶ ደግሞ ኢትዮጵያውያን እንደሚሆኑ ከኮርፖሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ በሁለተኛው ዓመት የሚሳተፉ ቻይናውያን ወደ 24 በመቶ ዝቅ እንደሚል፣ በሦስተኛው ዓመት ደግሞ ወደ 13 በመቶ፣ በአራተኛው ዓመት ኢትዮጵያውያን ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠሩት ይሆናል፡፡

በኮንትራቱ መሠረት ሁለቱ የቻይና ኩባንያዎች የፈጠሩት ጥምረት በሦስተኛው ዓመት ላይ የቻይናዋ ሸንዘን ከተማ የደረሰችበት የባቡር ቴክኖሎጂ ወደ አዲስ አበባ ሙሉ ለሙሉ ይዘዋወራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በመጨረሻዎቹ ሁለት የኮንትራት ዓመታት የቻይናዎቹ ኩባንያዎች ሚና ከኋላ ሆኖ የቴክኒክ ድጋፍ ማድረግ ብቻ ነው፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

በጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው ክስ ተሰማ

$
0
0

zone 9 bloggers

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው እየታየ ያሉት ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተው ክስ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው የክስ ዝርዝር ዛሬ በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሰምቷል፡፡

ዛሬ ህዳር 24/2007 ጠዋት በዋለው ችሎት፣ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ የቀረበው የክስ ዝርዝር በንባብ የተሰማ ሲሆን በክስ ወረቀቱ ላይ ከተመለከቱት ነጥቦች መካከል ግልጽ ያልሆኑ ነጥቦችን አካትቶ እንዲሰጥ ለአቃቤ ህግ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል፡፡ ስለሆነም ሙሉ የክስ ወረቀቱ አርብ ለጠበቆቹ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡

በጠቦቆቹ በኩል ክሱ ቀደም ብሎ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መሻሻሉን ለማረጋገጥ ያለፈው የፍርድ ቤቱ ብይን ግልባጭ እስካሁን እንዳልደረሳቸው በመግለጽ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የብይኑ ግልባጭ ሳይደርሰን ተሻሻለ የተባለው ክስ መሰማት የለበትም ብለው የነበር ቢሆንም፣ ክሱን አይታችሁ መቃወሚያ ካላችሁ አስተያየት እንድትሰጡበት እድል እንሰጣለን ያለው ፍርድ ቤቱ ክሱ እንዲሰማ አድርጓል፡፡

ፍርድ ቤቱ ጠበቆቹ ያላቸውን አስተያየት ይዘው እንዲቀርቡ ለታህሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል፡፡

“ከኦሮሚያ አንፃር፤ ከኢሕዴአግ ደርግ ይሻላል” –ዶ/ር መረራ ጉዲና

$
0
0

ዶ/ር መረራ ጉዲና በቅርቡ ባሳተሙት መጽሐፍ ላይ ምርጫ 97 እና ምርጫ 2002 በተመለከተ የራሳቸውን ግምገማ ማስፈራቸው የሚታወቅ ነው። ካሰፈሩት ነጥቦች እና መደምደሚያዎች አንፃር ቀጣዩን ምርጫ 2007 እንዴት ይመለከቱታል? ገዢው ፓርቲ እና ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በተመለከተ ምንስ ይላሉ? የኦሮሞ ሕዝብ ትግልን በተመለከተ ምን ይላሉ? ከተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኃይል አሰላፍ አንፃር የኦሮሞን ሕዝብ የፖለቲካ ሂደት እንዴት ይገልጽታል? የቀኝ ኃይሎች የፖለቲካ አካሄድን እንዴት ይረዱታል? እና ሌሎች ተያያዥ ጥያቄዎችን በማንሳት ተወያይተwል። ከዶ/ር መረራ ጉዲና ጋር ፋኑኤል ክንፉ ያካሄደው ቃለ-ምልልስ እንደሚከተለው ቀርቧል።
merara_gudina_vtim
ሰንደቅ፡-የኢትዮጵያን ምርጫ ሂደት “ምርጫ” እና “ቅርጫ” በሚል አባባል ሲገልፁ ይሰማል። ምን ለማለት ፈልገው ነው?
ዶ/ር መረራ፡-በሀገራችን በበዓላት የቅርጫ ሥጋ የመካፈል ባህል አለ። ቅርጫ ሲካፈል ሁሉም እንደ አቅሙ ይወስዳል። ትልቅ ብር የከፈለ ትልቅ ይወስዳል። ትንሽ ብር የከፈለ በከፈለው መጠን ድርሻውን ያነሳል። በኢትዮጵያ ምርጫ ግን አንድ ጎበዝ ሁሉንም ጠቅልሎ ይወስዳል። ይህን የተዛባ ሁኔታ ለመግለጽ ነው፤ ምርጫ እና ቅርጫ በሚል ለመግለጽ የፈለኩት።

ሰንደቅ፡- በመጽሐፍዎ፤ “በአፍሪካ ሀገር የመንግስት ጥያቄ የአቅም ጥያቄ ነው” በማለት ጽፈዋል። ፅንሰ ሃሳቡ ምንድን ነው?
ዶ/ር መረራ፡-አቅም ሲባል፣ ወታደራዊና ድርጅታዊ አቅም ነው። በተለይ ወታደራዊ አቅም። በአፍሪካ ወታደራዊ አቅም እስከሌለህ ድረስ በሕዝብ ድጋፍ ብቻ የመንግስት ስልጣን አታገኝም። ስልጣን ላይ አትወጣም። በተለይ ተቃዋሚ ከሆንክ ከእስር ቤት ወይም ከስደት አታመልጥም።
ሰንደቅ፡- ይህ የእርስዎ መሰረታዊ አስተሳሰብ ከሆነ፣ በ1997 ዓ.ም፣ በ2002 ዓ.ም አሁን ደግሞ በ2007 ዓ.ም ምርጫ መሳተፍ ለምን አስፈለጋችሁ? የፖለቲካ መጫወቻ ክፍት ቦታ እናገኛለን የሚልስ መነሻ እንዴት አገኛችሁ?

ዶ/ር መረራ፡-የምርጫ ፓርቲዎች በመሆናችን በምርጫው ገፍተናል። ወታደራዊ አቅምም ስለሌለን ከምርጫ ውጪ አማራጭ የለንም። ወደ ምርጫ የገባነው በጠቀስኳቸው ምክንያቶች እንጂ የፖለቲካ መጫወቻ ክፍተት እናገኛለን ከሚል መነሻ አይደለም።

ሰንደቅ፡- በመፅሐፍዎ ላይ፣ በምርጫ 97 እና በምርጫ 2002 የተቃዋሚውን ጐራ ያልሰራቸው የቤት ስራዎች መኖራቸውን አስፍረዋል። በተለይ የተቃዋሚው ጐራ በትብብር አንድ መሆኑንና ጠንካራ አደረጃጀት አለመያዙ ያስከፈለውን ዋጋ አንስተዋል። አሁንስ በ2007 ዓ.ም ምርጫ የተቃዋሚው ጐራ ይህን ስህተት አርሟል?

ዶ/ር መረራ፡- የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች ያላለፉት የታሪክ ፈተና፣ ማሸነፍ ያልቻሉት የታሪክ ፈተና በተለይም ተባብሮ የመስራት፣ አቅም ገንብቶ የመስራት፣ ልዩነቶችን አቻችሎ አብሮ የመስራት፣ ተባብሮ ገዢውን ፓርቲ የመግፋት ፖለቲካው አሁንም ድረስ ያላለፉት ታሪክ ፈተና ሆኖ ቀጥሏል። አሁንም አላለፍነውም። እንደውም ከ97 ጋር ሲተያይ ደከም ብለን የምንታይበት ሁኔታ ነው ያለው።

ስለዚህም ከአሁን ጀምሮ የተቃዋሚው ኃይሎች ቁጭ ብለው አሰላስለው ያለንበትን ሁኔታ መመልከት ተገቢ ነው። በተለይ ትግሉ ወደ ፊት እንዲገፋ የተሻለ ውጤት ለማምጣት ይህን የታሪክ ፈተና ለማለፍ በምንችልበት አቅጣጫ መንቀሳቀስ አለብን። ይህን የታሪክ ፈተና ማለፍ ካልቻልን የትም መድረስ አንችልም። ኢትዮጵያም የትም መሄድ አትችልም። እየተቋሰሉ፣ እየተጣሉ፣ እየተጠላለፉ በተተበተበ ፖለቲካ ውስጥ እየዋዠቁ መኖር፣ ለራሳችንም ሆነ ለሀገራችን የተሻለ ስራ እየሰራን እንዳልሆነ ይሰማኛል። የበለጠ ወደ ኋላ ቀርተናል።

ሰንደቅ፡- በመጽሐፍዎ በቀኝ ኃይሎች መቸገርዎን አስፍረዋል። እንደሚታወቀው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ም/ቤት ከመድረክ ጋር ያለውን ግንኙነት በገመገመበት ወቅት በብሔር ከተደራጁ ኃይሎች ጋር ለመስራት እንደማይችሉ ከስምምነት መድረሳቸው መዘገቡ ይታወቃል። ከዚህ አንፃር አሁንስ መድረክ ከቀኝ ኃይሎች ጋር ያለው ልዩነት እንደቀጠለ አድርገን መውሰድ እንችላለን ወይ?

ዶ/ር መረራ፡- አንድነት ውስጥ ያሉም ሌሎች በተቃዋሚ ጐራ ያሉ ጓደኞቼን ለመምከር ሞክሬአለሁ። ወደፊት ለመሄድ፣ ወንዝ ለሚያሻግር ፖለቲካ ለመስራት፣ የታሪክ ፈተናን ለማለፍ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች፣ የዴሞክራሲ ኃይሎች ነን የሚሉት ተባብረው ካልሰሩ፣ አቅም ገንብተው ካልሰሩ፣ የመቻቻል ፖለቲካ እስካልፈጠሩ ድረስ ለብቻቸው የትም አይደርሱም። ይህ በግልጽ መቀመጥ ያለበት ጉዳይ ነው። ከዚህ ውጪ ትርፉ ልፋት ብቻ ነው።
merera_gudina
ተባብረው ካልታገሉ አንድም ገዢውን ፓርቲ አስገድደው ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ እንዲቀበል ማስገደድ አይችሉም። ገዢው ፓርቲ እንኳን በድንገት ከስልጣን ላይ ቢወርድ የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመምራት የሚችሉበት ሁኔታ አይፈጠርም። ኢትዮጵያን ለሚቀጥሉት ሰላሳ ዓመታት አንድ ፓርቲ ለብቻው እገዛለሁ፣ አስተዳድራለሁ የሚለው ነገር ገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ ላይ ማብቃት አለበት። ኢሕአዴግ ሚሊዮን ሰራዊት ይዞ፣ የሀገሪቷን ሃብት ተቆጣጥሮ ሁሉንም ነገር ይዞ፣ ኢትዮጵያን በፈለገበት መንገድ መግዛት አልቻለም። ሃያ ሦስት ዓመት ለፋ እንጂ በሕዝብ ፈቃድ በተፈለገው መንገድ ማስተዳደር አልቻለም። ለሰላምና መረጋጋት በሚል ከፍተኛ የሀገሪቷ ሐብትም እየባከነ ነው የሚገኘው።

ከዚህ መለስ ያሉ ፓርቲዎች ደግሞ የሕልም ጉዞ ከመጓዝ ውጪ ኢሕአዴግ ከስልጣን አውርዶ የተሻለች ኢትዮጵያን፣ የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመፍጠር ከተፈለገ የግድ ተቃዋሚዎች ተባብረው መስራት አለባቸው። ልዩነቶችን አቻችለው ከወዲሁ የሞኝ ጉዞአቸውን አቁመው የተደቀነባቸውን የታሪክ ፈተና ለማለፍ መስራት አለባቸው። ይህን ማድረግ ካልቻሉ የትም አይደርሱም። ከዚህ ውጪ ያለው መንገድ አላስፈላጊ ሐብታችንን፣ ገንዘባችን እውቀታችንን ለማባከን ነው የሚሆነው። ተቃዋሚው ኃይል ከገቡበት የታሪክ እስር ቤት ሰብረው መውጣት አለባቸው። የዛሬ አርባ አመት ያልቻልነው ይሄንኑ ነው። ዛሬም ያልቻልነው ይህኑኑ ነው። ያ ቡድን… ይህ ቡድን… ነፃ ያወጣል የሚባለውን የሕልም ጉዞ መብቃት አለበት። በተባበረ ትግል ያልተመራ ተቃውሞ መጨረሻው፣ ሁሉንም ነገር በገዢው ፓርቲ በጎ ፈቃድ የሚወሰን ነው የሚሆነው። ይህን በግልፅ ማስቀመጥ ያስፈልጋል። በመጪው ምርጫ መታረም አለበት።

ሰንደቅ፡- የአረቡ ዓለም የፀደይ አብዮት ወደ ኢትዮጵያ ቢመጣም ሰፊ መሰረት ያለው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እስካልተዘረጋ ድረስ የፈለግነው ውጤት ላይ አያደርሰንም ብለዋል። ለዚህ መከራከሪያዎ የሚያነሱት ኀሳብ ምንድን ናቸው?

ዶ/ር መረራ፡- በግልፅ እየታየ ያለ ነገር ነው። ወደግራ፣ ወደቀኝ፣ ወደጎን፣ ወደላይ እየተሄደ ነው። ይህ የገመድ ጉተታ ፖለቲካም ኢሕአዴግ የልብ ልብ እየሰጠው ነው፤ በአላስፈላጊ መንገድም እንዲሄድ እያደረገው ነው፤ ራሳቸውንም ተቃዋሚዎቹን ገመድ ጉተታ ውስጥ ከቷቸዋል። ይህን የመሰለ የፖለቲካ ክፍተት ቀዳዳው ካልተሸፈነ ምንም አይነት ለውጥ ቢመጣ የትም መሄድ አይቻልም። ቀዳዳዎችን ደፍኖ ወደ አንድ መስመር መምጣት ከተቻለ መንግስትንም መለወጥ ይቻላል።

ዴሞክራሲ የሚባለው ብሔራዊ መግባባት መፍጠር ሲቻል ብቻ ነው። ሀገራችን እንዴት ትመራ? ምን አይነት ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ያስፈልገናል? የፖለቲካ መቻቻል የብሔር ብሔረሰቦች መብት? የፌደራሊዝም አይነት? ቁጭ ተብሎ መነጋገር ስትችል ነው። ይህ ባልሆነበት ሁኔታ ማንኛውም አይነት ለውጥ ቢመጣ ወደተፈለገው ዴሞክራሲያዊ ስርዓት አንደርስም። ለውጥ ቢከሰት የተለመደው የገመድ ጉተታ ፖለቲካ መከሰቱ አይቀሬ ነው። ለዚህ ጥሩ ማሳያ የግብፅ የፀደይ አብዮት ነው። ስልጣን ላይ ያለውን መንግስት አወረዱ፤ ቢያንስ እስከ ማውረድ ተስማምተው ነበር። በዚህ መልኩ ከእኛ ይሻላሉ።

ከለውጡ በኋላ ግን እያየን ያለነው የሙባረክ ወታደሮች ናቸው፤ ሃገር እየገዙ ያለው። ይባስ ብለው ሙባረክን ነፃ አውጥተው ለለውጥ የተነሱ ኃይሎችን እየገደሉ፣ እያሰሩ ይገኛሉ። ለዚህ ምክንያቱ የለውጥ ኃይሉ ሙባረክን እስከማውረድ እንጂ ቀጣይ የግብፅ መንግስት እና ሕዝብ እንዴት መመራት እንዳለባቸው የደረሱበት ስምምነት አልነበረም። የለውጡ ኃይል ብሔራዊ መግባባት አልነበረውም። በተመሳሳይ መልኩ በዚህም ሀገር ተመሳሳይ ለውጥ ቢከሰት ኢሕአዴግን ከማውረድ በዘለለ የተደረሰ ብሔራዊ መግባባት ባለመኖሩ ተመሳሳይ ዕጣ ፈንታ ሊከስት የሚችልበት እድል ሰፊ ነው። እንደው ጠዋት እና ማታ አንድነት፣ አንድነት ስለተባለ ብቻ ቀውስ ማቆም አይቻልም። የወደፊቷ ኢትዮጵያ ምን መምሰል እንዳለባት አሁን ላይ ነው ምላሽ መስጠት ያለባቸው፣ አሁን ላይ ነው መግባባት መተባበር የሚያስፈልገው። ቢያንስ ምን አይነት የፖለቲካ ስርዓት ያስፈልጋል? ምን አይነት ፌደራሊዝም ያስፈልጋል? የሁሉም አስተዋፅኦ ምን መሆን አለበት? ለዚህም ነው ኢሕአዴግ ተገፍቶ እንኳን ከስልጣን ቢወርድ ይህን ታሪካዊ ፈተና እስካላለፍን ድረስ የተረጋጋ የፖለቲካ ስርዓት መፍጠር አንችልም የሚለውን መናገር እፈልጋለሁ። ፖለቲካ እስከገባኝ ድረስ ለውጥ ውስጥ ያሉ ኃይሎችም እንዲረዱኝ የምፈልገው ይህንኑ እውነት ነው።

እንደተባለው አንዳንድ የፖለቲካ ኃይሎች ከዚህ ቡድን ጋር፣ ከዛ ቡድን ጋር አልሰራም አሉ ነው የተባለው። ከመስራት ውጪ ምንም አማራጭ የላቸውም። ሌላው አማራጫቸው ኢትዮጵያን ማጥፋት ብቻ ነው። እድልም ቢገጥማቸው እና ወደስልጣን ቢጠጉ ኢትዮጵያን ቢያጠፉ እንጂ ከሌሎች የፖለቲካ ኃይሎች ጋር ተባብረው በመሀል መንገድ ላይ ካልተገናኙ በስተቀር ኢትዮጵያን የትም አይወስዷትም። ለምሳሌ ከእኛ አይነት የፖለቲካ ኃይል ጋር ካልሰሩ፣ ከነፃ አውጪ ድርጅቶች ጋር ምን ሊሆኑ ነው? ከኦነግ፣ ከኦብነግ፣ ከጋምቤላ ነፃ አውጪ ግንባሮች ጋር ምን ሊያደርጉ ነው? ስለዚህም መሬት ላይ ያለውን የኃይል አሰላለፍ ምንድን ነው ብሎ መፈተሸ ተገቢ ነው የሚሆነው። ከዚህ ውጪ ለመብታቸው የሚታገሉትን ጡረታ ለማስወጣት ከሆነ መጀመሪያ ጉልበቱ እንዳላቸው ማረጋገጥ ነው። ጉልበት እንኳን ቢኖራቸው ደርግ የኤርትራን ጥያቄ ገፍቶ ገፍቶ አሁን ወደላበት ደረጃ እንዳደረሰው ሁሉ፤ እነዚህም የቀረችውን ኢትዮጵያ ገፍተው ለሁላችን የማትሆነውን ኢትዮጵያ ለመፍጠር ካልሆነ በስተቀር ሌላ ነገር ያላቸው አይመስለኝም። ለዚህም ነው የመተባበር፣ ሰጥቶ የመቀበል፣ የመቻቻል ፖለቲካ ውስጥ መግባት ካልተቻለ ቢያንስ ቢያንስ ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን አናገኛትም። ምን አልባትም ከዚህ የበለጠ አደጋ ሊመጣ ይችላል። ኢትዮጵያን የሚበታትን አደጋም ሊፈጠር ይችላል።
Dr merera gudina Book
ሰንደቅ፡- በመፅሐፍዎ መደምደሚያ ሶስት ምክረ ኀሳብና ወቀሳ አስቀምጠዋል። ከእነዚህ ውስጥ “የትግራይ ሊሂቃን ስልጣን ወይም ሞት የሙጥኝ” ብለዋል የሚለው አንዱ ነው። ለዚህ አገላለፅዖ ማሳያው ምንድን ነው?

ዶ/ር መረራ፡- በግልፅ ነው የሚታየው። የኢትዮጵያን ዋና የስልጣን መዘውር የያዙት እነሱ ናቸው። በየትኛውም ሁኔታ ብትወስደው በበላይነት እነሱ ናቸው የሚመሩት።

ሰንደቅ፡- የኢትዮጵያን መንግስት የሚመራው በሚኒስትሮች ምክር ቤት ነው። በዚህ ምክር ቤት ውስጥ እርስዎ ከሚሏቸው የትግራይ ሊሂቃን ከሶስት አይበልጡም። ከዚህ አንፃር ድምዳሜዎትን እንዴት ያዩታል?

ዶ/ር መረራ፡- ብዙ ዝርዝር ውስጥ ሳልገባ ቁልፍ ስልጣንም ያላቸው፣ የመወሰንም ስልጣን ያላቸው ተቋማቱንም የሚያንቀሳቅሱት የሚያስወስኑትም በዋናነት ከትግራይ የመጡ ሊሂቃን ናቸው ለማለት ነው።

ሰንደቅ፡- የአማራው ሊሂቃን አሁንም ድረስ “ከበላይነት አስተሳሰባቸው መላቀቅ አልቻሉም” ብለዋል። ከአማራው ሕዝብ የወጡ ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን በዚህ አገላለጽዎ እንዴት ያስተናግዷቸዋል?

ዶ/ር መረራ፡- የአማራ ሕዝብ ትላንትም ዛሬም ሲጨቆን አውቃለሁ። እዚህ ላይ ጠብ የለኝም። ዋናው ጉዳይ እኔ ፖለቲካ እስከገባኝ ድረስ የአማራ ሊሂቃን የበላይነት አስተሳሰቡ አለቀቀውም። ከሌሎች ኃይሎች ጋር ብሔራዊ መግባባት ፈጥሮ እናንተም እንዲህ ሁኑ እኛም መሐል መንገድ ላይ እንመጣለን ብሎ በጋራ ለመስራት እና ልዩነቶችን መሃከል ላይ አድርሶ የመታገል ፍላጎት አላይባቸውም። ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነው በጎሳ የተደራጁ በምን የተደራጁ ቡድኖች ጋር አንሰራም የሚለው የአማራው ሊሂቃን አስተሳሰብ፣ ከማን ጋር ሊሰሩ ነው? ስለዚህም የዛሬይቱን ኢትዮጵያ ተቀብሎ በጋራ መስራት ነው የሚያስፈልገው። እኔ በግሌ ሂሳብ የማወራረድ ፖለቲካ አልፈልግም። ሆኖም ግን አንድ የተወሰነ ማሕበረሰብ ተበድያለሁ ሲል አልተበደልክም የሚል ድርቅ ያለ መከራከሪያ ከማንሳት ቢያንስ ወደፊት ማንም የማይበደልበት ሀገር እንግባ ማለት የተሻለ ነው የሚሆነው። አዲስቷን ኢትዮጵያ ለመፍጠር መስራት ነው የሚጠበቅባቸው።
ሰንደቅ፡- የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ውስጥ ያሉ የአማራ ሊሂቃን የአማራ ሕዝብ እንደማንም የተጨቆነ፣ ኋላ የቀረ ሕዝብ መሆኑን ተረድተው ከሌሎች ብሔሮች ጋር ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት እየታገሉ እንደሚገኙ የድርጅታቸውም ሰነድ ሆነ ሊሂቃኑ በአደባባይ የሚናገሩት ነው። የአማራ የበላይነት መጠበቅ አለበት ሲሉም አይደመጡም። ከዚህ አንፃር ድምዳሜዎ ሁሉኑም የአማራ ሊሂቃን ማጠቃለሉን እንዴት ያዩታል? ብአዴን እየተጠቀመ ያለውን የፖለቲካ መጨወቻ ሜዳስ (political space) እንዴት ይገልጽታል?

ዶ/ር መረራ፡- ብአዴን የሚሰራው በዚህች ሀገር ውስጥ የበለጠ ችግር የሚፈጥር ነው። ምክንያቱም የሚያስፈጽሙት የኢሕአዴግ ፖሊሲዎችን ነው።
ሰንደቅ፡- ኢሕአዴግ ከመሰረቱት ፓርቲዎች አንዱ ብአዴን ነው። ስለዚህም ራሱ የተሳተፈበትን ፖሊሲ ማስፈጸሙ እንዴት ጉዳት ይሆናል?
ዶ/ር መረራ፡- ብአዴን ትንሽ ከኦህዴድ ይሻል ይሆናል እንጂ የተለየ ሚና የላቸውም። ከዚህ ውጪ የአንድ መንግስት አስፈፃሚዎች ናቸው። እኔ እስከሚገባኝ ድረስ ከዚህ የዘለለ ሚና የላቸውም።

ሰንደቅ፡- እርስዎ ካስቀመጡት መደምደሚያ መነሻነት ወስደን፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ለውጦች አሉ። በማሕበራዊም በፖለቲካውም አንፃራዊ ለውጦች አሉ። በብቸኛ መንግስትነት ያስቀመጡዋቸው “የትግራይ ሊሂቃን” እነዚህን ተግባሮች በዚህች ሀገር ውስጥ መፈጸማቸው ከምን መነሻ የመጣ ነው? በእርስዎ አረዳድ የትግራይ ሊሂቃን በኢትዮጵያ ውስጥ የተለየ ተልዕኮ ወይም ራዕይ አላቸው ብለው ያስባሉ?

ዶ/ር መረራ፡- ብዙ ዝርዝር ውስጥ ሳልገባ እነዚህ ኃይሎች በሀገሪቷ ውስጥ ብሔራዊ መግባባት ካልፈጠሩ፣ ሀገሪቷን ወደ ብሔራዊ ዕርቅ ካልመሩ፣ ሀገሪቷን ወደ ብሔራዊ ስምምነት ካልመሩ መጪው ጊዜ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ብሩህ ነው የሚል ግምት የለኝም።

ሰንደቅ፡- ገዢው ፓርቲ ብሔራዊ ዕርቅ ጉዳይ ሲነሳ የተለያዩ የፖለቲካ አስተሳሰቦችን ከማስታረቅ ጋር መያያዝ የለበትም። በፖለቲካ መስመርም የተጣላ የለም የሚል መከራከሪያ ያነሳል። በዚህ ላይ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?

ዶ/ር መረራ፡- እንደዚህ እያሉን ኢሕአዴግ እንዲሁም በበላይነት የሚመራው ህወሓት ተጣልተው አገኘናቸው። ለምሳሌ ሕወሃት ብትወስድ አንዱን ጎኑ በልቶ ነው ስልጣን ላይ ያለው፣ የቆየው። እነአቶ ተወልደ የመለስ ሁለተኛ ሰው ነበሩ። አቶ ስዬ የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ነበር። አቶ ገብሩ አስራት የትግራይ መስተዳድር ፕሬዝደንት ነበረ። ከዚህ አንፃር ግማሽ ጎኑን በልቶ ሕወሃት ስልጣን ላይ የቆየው። ብሔራዊ ርዕቅ ለራሱም ለኢሕአዴግ ያስፈልጋል። እነዚህ ሰዎች ኢሕአዴግ ከጫካ ሚኒሊክ ቤተመንግስት ድረስ ያመጡ ሰዎች ናቸው። አሁን ከሚታዩት ባለስልጣናት የበለጠ ዋጋ የከፈሉ ናቸው። ስለዚህም የተጣለ የለም የሚሉት ቀልድ ነው። ቀልዳቸውን መቀጠል ይችላሉ።

በድርጅቶች ደረጃ ከወሰድነው ላለፉት አርባ አመታት የተቋሰሉ ድርጅቶች ያለባት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለነው። በማሕበረሰብ ደረጃም ከወሰድነው ብዙ ቅራኔዎች እንዳሉም እናውቃለን። ስለዚህም የተጣለ የለም እየተባለ ግጭት በአፍጫችን ላይ ጠዋት እና ማታ እየፈነዳ ነው ያለው። ለምሳሌ በጉራፈርዳ፣ በመዠንገር፣ በጋምቤላ፣ በሱማሌ እና በኦሮሚያ አካባቢዎች ግጭቶች ተነስተዋል። ሰዎችም ተፈናቅለዋል። ነገር ግን ጉዳዩ ተዳፍኗል።

ሰንደቅ፡- የእርስዎ መከራከሪያ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ እስካሁን ካለፍናቸው መንግስታት ለኦሮሚያ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን በመዘርጋትና ተጠቃሚ በማድረግ አሁን ያለው መንግስት የተሻለ መሆኑን አንስተው የሚከራከሩ ምሁራን አሉ። እርስዎ ከዚህ አንፃር እንዴት ነው የሚመለከቱት?

ዶ/ር መረራ፡- የምትላቸው ወገኖች ምን ያህል ፖለቲካ ገብቶአቸው ይሁን አልገባቸው አላውቅም። ለምሳሌ ደርግ እና ኢሕአዴግን እንውሰድ። በኢትዮጵያ ደረጃ በተለይ በሰሜኑ ክፍል ደርግ ከሁሉም የኢትዮጵያ መሪዎች የባሳ ሊሆን ይችላል፤ ለኦሮሚያ ግን አልነበረም። እኔን ብትወስደኝ በደርግ ሰባት አመታት ታስሬያለሁ። ከእኔ ጋር መኢሶን ውስጥ የተገደሉም አሉ። በተወሰነ ደረጃ በኦነግም ውስጥ የነበሩ የተገደሉ አሉ። ግን በሰፊው ሲታይ በደርግ ጊዜ ከነበረው ይልቅ ኦሮሚያ ውስጥ አሁን ያለው ቀውስ ይበዛል። አሁን ያለው እስር ይበዛል። እስር ቤት ብትሄድ የእስር ቤት ቋንቋ ኦሮሚፋ ነው የሚባለው ለዚህም ነው።

በተለይ በስፋት ከወሰድነው ደርግ እና ኢሕአዴግን አታወዳድርም። በዚህ ዘመን በኦሮሞ ሕዝብ ላይ የደረሰውን በደል አታመዛዝነውም። በኢትዮጵያ ደረጃ ቀይ ሽብር ከወሰድክ የደርግ በደል ወንጀል አፈና ይበዛል። የበለጠም ነው። በኦሮሞ ደረጃ ግን ሁለቱን ስርዓቶች ስታወዳድረው በሚታሰረውና በሚገደለው ብዛትና በደረሰው መፈናቀል እና ሌሎችም ነገሮችን ስታይ የኢሕአዴግ ይብሳል የሚል እምነት አለኝ። ደርግ ምንም ይሁን ምንም የኢትዮጵያ ንቅናቄ ስጦታም ቢሆን መሬት ላራሹ በአብዛኛው ኦሮሞና የተቀረውን የደቡብ ሕዝብን ከጭሰኛነት አውጥቶታል፣ ጠቅሞታልም። በሌላ በኩል ደርግ ሁላችንንም ገድሏል። ወንድሜንም ገድሏል።

ሰንደቅ፡- ካስቀመጡት መከራከሪያ በመነሳት፣ ኦህዴድ ለኦሮሞ ሕዝብ የሰራው ስራ የለም ብሎ መደምደም ይቻላል?
ዶ/ር መረራ፡- እኔም ሆንክ በሌሎች የኦሮሞ ሙሁራን ኦህዴድ የሚታወቀው፣ የኦሮሞን ሕዝብ በማዘረፉ፣ ሕዝቡን በማሳሰሩ፣ ሃብት በማስቀማቱ ነው። አሉታዊ በሆነ መልኩ ነው የሚታወቀው። የኦሮሞን ልጆች መብት በማስጠበቅና በማጎናጸፍ አይታወቅም። ይህን ስልህ በቀድሞ የኦህዴድ ባለስልጣናት ጭምር የተረጋገጠ ነው። በተለይ ከፓርቲው ከተለዩ በኋላ የሚሰጡት ለኦሮሞ ሕዝብ ውክልና እንዳልተሳካለት ነው።

ሰንደቅ፡- በኦህዴድ ፖለቲካ አመራር ክልሉ በቋንቋው እንዲጠቀም፣ የፍትህ ስርዓቱንም በቋንቋው እንዲዳኝ፣ ክልላዊ መንግስት እንዲኖረው፣ መሬቱን የማስተዳደር ስልጣን፣ መሰረተ ልማቶችን የመገንባቱ ስራዎች በመልካም ጎኑ ሊወሰድ አይችልም?

ዶ/ር መረራ፡- ዋናው ጉዳይ የኦሮሞን መብት ጥቅም እናስከብራለን የሚሉ የኦሮሞ ኃይሎች እይታቸው ነው ችግሩ። የኦሮሞ ሕዝብ እነዚህ ኃይሎችን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ፈጥረውልኛል ብሎ ይመለከታቸዋል ወይ? መብትና ክብሬን እያስጠበቁ ነው ብሎ ይመለከታል ወይ? ሕዝብ ይህን መመስከር ካልቻለ ዋጋ የለውም። በቃለ መሃላ ብቻ እናደርጋለን ማለት የትም አያደርስም። ውሃም አይቋጥርም። እነሃሰን አሊ፣ አልማዝ መኮ፣ ጁነዲን ሳዶ፣ እንዲሁም ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳን ጨምሮ ኦህዴድ የሚለውን የሚተገብር ሳይሆን ሕዝቡን የሚያስጠቃ ነው ብለዋል። ሕዝቡን ከመሬቱ እያፈናቀለው ነው። ሃብቱን እያዘረፈው ነው። በቀድሞ የኦህዴድ አመራሮችም በሕዝቡ ውስጥ ያለው አመለካከት ይህ ነው። ስለዚህም ኦህዴድ የሚለው ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ሳይሆን የሞግዚት አስተዳደር ነው በኦሮሚያ ያለው። ችግሩ እዚህ ላይ ነው።

ሰንደቅ፡- በመፅሐፍዎ ላይ ኦነግን በተመለከተ ካልተነካካን በስተቀር ለሶስተኛ ወገን ብለን አንጋጭም ብለዋል። ይህ ምን ማለት ነው?
ዶ/ር መረራ፡- ኦነግን በተመለከተ እኛ የተለየ አቋም እንዳለን ይታወቃል። እነሱም ያውቃሉ። ሆኖም ግን የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ መብቱ እስከሚጠበቅለት ድረስ ለምን በዚያ፣ በዚህ መስመር ሄደው ታገሉ ብለን የምናገልበት ሁኔታ የለም። እነሱን ወደመግፋት መጣላት ውስጥ አንገባም ለማለት ነው። ዋናው ጉዳይ የኦሮሞ ሕዝብ ለነፃነቱ ለክብሩ እየታገለ ነው የሚገኘው። የተለያዩ የኦሮሞ ድርጅቶች ደግሞ በተለያየ ስትራቴጂ ፖሊሲ እየታገሉ ነው የሚገኙት። ስለዚህ በተቻለ መጠን የእኛ ድርጅት ካልተነካ እነሱ እኛ ላይ ድንጋይ ካልወረወሩ ከመሬት ተነስተን ለኦሮሞ ሕዝብ እንታገላለን ስላሉ ብቻ አንጋጭም። እንደስትራቴጂም አንከተለውም።

ሰንደቅ፡- በአንፃሩ ግን በመጽሐፍዎ ላይ፣ የኦሮሞ ሕዝብ እንደኦህዴድ ለሌሎች ኃይሎች የኃይል ሚዛን መጠበቂያ መሆን የለበትም ብለዋል። የዚህስ መነሻ አመለካከቶ ምንድን ነው?
ዶ/ር መረራ፡- ደጋግሜ እንደምለው የኦህዴድ ባለስልጣናት የኦሮሞን ሕዝብ ጥቅም ከማስከበር ወደ ማስጠቃት፣ ከቤት ንብረታቸው ማፈናቀሉ፣ በአዲስ አበባ ዙሪያ እንኳን በመቶ ሺዎች የሚሆኑ የኦሮሞ ልጆች ተፈናቅለዋል። በሺዎች ታስረዋል። ስለዚህም ነገ ከነገ ወዲያ አይጠቅማችሁም። የተወለዳችሁት ከኦሮሞ ልጆች ነው። የሚቀብራችሁ የኦሮሞ ሕዝብ ነው። ያደጋችሁት የኦሮሞን ሕዝብ ወተት እየጠጣችሁ ነው። ሕዝባችሁን ለጊዜያዊ ጥቅም ብላችሁ አትጉዱ። እነዚህን ሌሎችን ለመፈጸም መሳሪያ አትሁኑ ለማለት ፈልጌ ነው።

ሰንደቅ፡- አሁን ካለው መንግስት በጠንካራ ጎን የሚያነሱት ይኖርዎት ይሆን?
ዶ/ር መረራ፡- ሲመጡ የገቡት ቃል ኪዳን ጥሩ ነበር። የብሔረሰቦችን እኩልነት እናመጣለን። ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እናመጣለን። የእዝ ኢኮኖሚን አስወግደን በተሻለ መንገድ የገበያ ስርዓት እንድንመራ እናደርጋለን ያሏቸው ቃል ኪዳኖች በጣም ጥሩ ነበሩ። በኋላ ላይ የሄዱበት መስመር ነው ከኢሕአዴግ የለያየን። ኢሕአዴግ ስልጣን ላይ ሲወጣ ደጋፊው ነበርኩ። በመጸሐፌም አስፍሬዋለሁ። የተለያየነው የሽግግር መንግስት ምስረታ ላይ በተፈጸመው ቲያትር ነው። ያለፉት መንግስታት ሲሰሩት የነበረውን ድራማ አይናችን እያየ ደገመው። ከዚህ በኋላ ኢሕአዴግ የትም አይደርስም የሚል መደምደሚያ ላይ የደረስኩት ለዚህ ነው።
ቢያንስ ቢያንስ ግን ደርግን ስንታገል ለነበርነው ኃይሎች ደርግን ማስወገዳቸው በየትኛውም ሚዛን ትልቅ ድል ነው። ግን ደርግ የሰራውን ስህተት በቪዲዮ እያየ እሱኑ መድገሙ ትልቅ ወንጀል ነው። ይህን ስህተት ካላረመ ከደርግ የተሻለ የታሪክ ስፍራ ይኖረዋል የሚል ግምት ለመስጠት ያስቸግራል።

ፀረ-ኢትዮጵያዊውና ዘረኛው ወያኔ በኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ስም አይነግድም!

$
0
0

prd_4ba1e0c3ae741የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ቅጥረኛ የሆነው ፀረ-ኢትዮጵያዊውና ቅኝ-ገዥው ወያኔ ባሕር ማዶ ተሻግሮ በሃገረ አሜሪካ ኮለምበስ ኦሃዮ “በስሜን አሜሪካ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች የባሕል ክብረ በዓል” በሚል ስም እሑድ ኅዳር 28 ቀን 2007 ዓ/ም ( Sunday, December 7, 2014 ) ከቀኑ 1:00pm ጀምሮ በሃያት ረጀንሲ ሆቴል (Hyatt Regency Hotel @ 350 North High Street, Columbus, OH 43215) ለማክበር በዝግጅት ላይ ይገኛል። ለዚህ በዓል መሰናዶ፤ ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የወያኔ ኢምባሲ የበላይ መሪ በመሆን፤ በአካባቢያችን ያሉትን የለየላቸው ከሃዲዎችና የባንዳ ልጆችና የልጅ ልጆች በአስተባባሪነት በማሰለፍ ነው።  —--[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—--

 


ፓርቲዎች በምርጫ አንሳተፍም ቢሉ….. 

$
0
0

በምርጫ አለመሳተፍ መብት ነው !በኢትዮጵያ ያለው ጭላንጭል የፖለቲካ ምኅዳር ሲታይ፣ይህ ውሳኔ የሕግ፣የፖለቲካ እና የሞራል ድጋፍ አለው፡፡ሆኖም ግን በምርጫ ያለመሳተፍ መብት በራሱ-የራሱ የሆነ ተግዳሮቶች አሉትና፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የትርፍ-ኪሳራ ሥሌት የግላቸው ነው የሚሆነው፡፡

 

ይድነቃቸው ከበደ

(ይድነቃቸው)

(ይድነቃቸው)

ይህ ጹሑፍ በምርጫ አለመሳተፍ መብት መሆኑን ከህግ አንፃር ለማየት እንጂ፣ የሚጪው አገረ አቀፍ ምርጫን አስመልክቶ “ኢሕአዴግ ለመርጫ አልተዘጋጀም !” እና “የ24 ሰዓት ተቃውሞ በአዲስ አበባ !” በሚል ዕርሶች ከዚህ በፌት በፃፍኳቸው ፁሑፍ የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ፣ ገዥው መንግስት ለነፃ እና ፍትሃዊ ምርጫ እራሱን አዘጋጅቶ፣ ውጤታማ ምርጫ ማካሄድ እንደማይቻል የግል እምነቴን ገልጫለው፡፡

ወደተነሳሁበት ዕርስ ስገባ፡- ማንኛውም ሰው በፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ እንዲሳተፉ አይገደድም፣ባለመሳተፉ ግን ተቃውሞን የመግለፅ እና ደግፋ የመስጠት መብት ይነፈጋል ማለት አይደለም ፡፡ይህም በመሆኑ የትኛውም የዲሞክራሲ ሥርዓት የተሟላ ተሳትፎ በህብረተሰብ ካልተደረገበት ውጤታማነቱ ደካማ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡የዲሞክራሲ ሥርዓት ማሳያ መስታዎት ከሆኑት ውስጥ አንዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በነፃነት መንቀሳቀስ ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ያለምንም ፍርሃት በፈለገው ወይም በፈለገችው ፓርቲ ውስጥ አባል የመሆን ዕድልና አማራጭ ማግኘት የግለሰብ መብት ነው፡፡ግለሰቦች በፈለጉት የፖለቲካ ፓርቲ የመደራጀት እና የመሳተፍ ነፃነት ሲኖራቸው ለዲሞክራሲ መሠረት ይሆናል፡፡

ይህ አይነቱ የዲሞክራሲ ሥርዓት በአገራችን ምን ያኸል ተፈፃሚ ነው ? ተብሎ ቢጠየቅ ምላሹን ለማወቅ ብዙም አድካሚ አይደለም፡፡ውጤቱ አሉታዊ ነው፡፡እርግጥ ነው በሕገ መንግስት አንቀፅ 31 ማንኛውም ሰው ለማንኛውም ዓለማ በህግ “የመደራጀት” መብት እንዳለው በግልፅ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ይሄን መነሻ በማድረግ በአገር አቀፍ እና በክልል ደረጃ የተቋቋሙ የፖለቲካ ፓርቲዎች መኖራቸው የሚታወቅ ነው፡፡የእነዚህ ፓርቲዎች መብት እና ግዴታ እንዲሁም ሊከተሏቸው የሚገባ መርህዎች፣ በሕገ መንግስቱ፣በፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ አዋጁች እዲሁም በመተዳደሪያ ደንብቻው ብቻ ነው፡፡

በዚህም መሠረት ተቋቁመው እየተንቀሳቀሱ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በአገራችን ቁጥራቸው በርካታ ቢሆንም፣ ቢሚፈለገው ሁኔታ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ግን በቁጥር አነስተኛ ፓርቲዎች ሲሆን፣ የተቀሩት የምርጫ መጣ ወይም የመግለጫ አሯሯጮች pacemaker መሆናቸው በግልፅ የሚታወቅ ነው፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ዋንኛ ዓላማ በመርጫ ተወዳድረው በማሸነፍ የፓለቲካ ሥልጣን በመያዝ የቆሙለት ዓላማ በስልጣን ዘመን ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡

ምርጫ በዲሞክራሳዊ አካሄድ ለሚወከል መንግስት የጥንካሬ መለኪያ ነው፡፡ይህን ለማለት የሚያስችለው ተመራጮች መብታቸው እና ግዴታቸውን ሙሉ በሙሉ ከመራጩ ሕዝብ ስለሚያገኙት ነው፡፡እንዲ አይነቱ በሕዝብ ተሳትፎ ሥልጣን የሚቀየርበት ዋናው መንገድ ነፃና ሚዛናዊ የሆነ ምርጫ ሲደረግ ብቻ ነው፡፡ በአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ በኢሕአዲግ/ በህወሐት መንግሰት የ24 ዓመት የስልጣን ዘመን በተደረጉ ምርጫዎች ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለመሆን አልቻለም፡፡ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ በዋነኛነት የሥርዓቱ አስከፊ ድርጊት ቢሆንም፣ በተጨማሪ ጠንካራ የሆኑ በመላው ኢትዮጵያ የሕዝብ ድጋፍ ያለው የተቃዋሚ ፓርቲ አለመኖሩም ጭምር ነው፡፡ እርግጥ ነው በ1997 ዓ.ም በቅንጅት የታየው የተቃዋሚ ፓርቲዎች መነቃቃት፣ በአገራችን የዲሞክራሲ በዓል አንድ እርምጃ ወደፊት ከነበረበት ያንቀሳቀሰው ቢሆንም፣ በገዥው ሥርዓት ቀጥተኛ ተፅኖ፣ እንዲሁም በቅንጅት ፓርቲ ውስጥ በታየው ድክመት እና የስልጣን ሽኩቻ የለውጥ እንቅስቃሴውን ገትቶታል፡፡

አሁን ላይ በአገራችን የሚንቀሳቀሱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ከበፊቱ “በቆምክበት እርገጥ” አይነት የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተላቀው ምን ያህል “ወደፊት” እየሄዱ ነው የሚለውን ምላሽ ይህን ጹሑፍ ለሚያነቡ እና ለጉዳዩ ቅርብ ነኝ ለሚሉ ወገኖች የምተወው ሃሳብ ነው፡፡ ሆኖም ግን በአገር ውስጥ የሚንቀሣቀሱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከ6 ወር በኋላ አገር አቀፍ ምርጫ ይጠብቃቸዋል፡፡ፓርቲዎች የምርጫ ፓርቲ ቢሆኑም ፣በምርጫ አለመሳተፍ መብታቸው በሕግ የተጠበቀ መሆኑን አውቀው ግራ ቀኛቸውን ቢመለከቱ፣ዝም ብሎ ገዥውን ፓርቲ በምርጫ ከማጀብ ይላቀቃሉ፤አሊያም በእኩል ተሳትፎ ወደ ምርጫው የሚገቡበትን መንገድ ተገዳድረው ማመቻቸት ይቻላል፡፡

የተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ አዋጅ ቁ .573/2000 አንቀፅ 39 ቁ.2 ሐ.“ የፖለቲካ ፓርቲ ለሁለት ተከታታይ የምርጫ ዘመን የጠቅላላ ወይም የአካባቢ ምርጫ ወድድርን ሳይሳተፍ የቀረ እንደሆነ ” ምርጫ ቦርድ በአዋጁ መሠረት ውሳኔ በማስተላለፍ ከመዝገብ ሊሰርዝ ይችላል፡፡የሚል የህግ ድንጋጌ አለ፣ይህን ድንጋጌ ከተነሳንበት ዓላማ ጋር በማገናኘት ምክንያት እና ውጤቱን መመልከት ተገቢ ነው፡፡

በመሠረቱ የፓርቲ ነፃነት በእንዲ መልኩ መገደብ አጠቃላይ የአዋጁ ችግር ዋንኛ ማሳያ ነው፡፡የትኛውም ፓርቲ በምርጫ የመሳተፍ ወይም ያለመሳተፍ መብት ካለጊዜ ገደብ ለራሱ ለፓርቲ የሚተው ስራ እንጂ ፣በህግ ገደብ የተጣለበት መሆን የለበትም፡፡ይህን ለማለት የሚያስደፍረው የግል እንዲሁም የጋራ መብት የሚጋፋ በመሆኑ ነው፡፡ለዚህም ማሳያ የመምረጥ እና ያለመምረጥ መብት የተጠበቀ ነው፡፡ ለምሳሌ እኔ በመጪው ምርጫ አልመርጥም ፣አልመረጥም ይህ በህግ ክልከላ ተደርጎብኝ ሳይሆን የእኔ መብት በመሆኑ ነው፡፡ልክ እንደኔ የግል መብት ያላቸው ሰዎች ተሰባበስበን የጋራ መብታችን ለማቋቋም በምንቀሳቀስበት ወቅት በግሌ ማድረግ የምችለውን በጋራ እንደማጣት ይቆጠራል፡፡ከዚህ አንፃር ይህ ድንጋጌ በእኔ እይታ ተገቢ መስሎ አይታየኝም፡፡

አሁን ባለው ነባራዊ ሃቅ በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች የሚተዳደሩት በዚህ አዋጅ ነው፡፡በመሆኑም አዋጆን መሠረት በማድገረግ በምርጫ አለመሳተፍ ገደብ ቢኖረውም ለፓርቲዎች የተሰጠ መብት አለ፡፡ ማንኛው ፓርቲ ለሁለት ተከታታይ የምርጫ ዘመን ሳይሳተፍ የቀረ እንደሆነ ይሰረዛል፡-ይህ ማላት፣በ2002 አገር አቀፍ ምርጫ በማንኛውም ምክንያት በምርጫ ያልተሳተፈ “ሀ” የተባለ ፓርቲ በ2007 የማይሳተፍ ከሆነ ይሰረዛል ማለት ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ይሄ “ሀ” የተባለው ፓርቲ በ1997 ምርጫ አልተሳተፈም ብንል ፣በ2002 ተሳትፏል ካልን በ2007 ምርጫ አለመሳተፍ የ”ሀ”ፓርቲ መብት ነው፡፡ይህም በማድረጉ ከምርጫ ቦርድ ምን አይነት ጥያቄ ለዚህ ፓርቲ አይቀርብም፡፡በዚህ መሠረት ፓርቲዎች ለሁለት ተከታታይ የምርጫ ዘመን በምርጫ ካተሳተፉ የመሰረዝ እጣቸው በእጃቸው ነው፡፡ሆኖም ግን የምርጫ ዘሙኑ ተከታታይነት ሳይኖረው በምርጫ አለመሳተፍ በአዋጁ መሠረት የሚያስከትለው ውጤት አይኖረውም፡፡

ይህ ከላይ የቀረበው ማሣያ፣ ለአገር አቀፍ እንዲሁም ለአካባቢ ምርጫ የሚያገለግል ነው፡፡በአሁን ወቅት ሁለቱ ምርጫዎች በተመሳሳይ የምርጫ ዘምን ባለመካሄዳቸው እረሳቸውን ችለው የሚቆጠሩ የምርጫ ዘመን ነው፡፡በኢትዮጵያ አሁን ባለው የምርጫ ስርዓት ፣የአንድ የምርጫ ዘመን አምስት ዓመት ነው፡፡ስለዚህም በአገር አቀፍ እና በአካባቢ የምርጫ ዘመን የ2 ዓመት ልዩነት አለ ማለት ነው፡፡በመሆኑም በዘንድሮ የአገር አቀፍ ምርጫ ዘመን ከባለፈው ሁለት ዓመት ከተካሄደው የአካባቢ ምርጫ ዘመን ፈፅሞ የሚገኛኝ አይደለም፡፡

በሕገ መንግሥት አንቀፅ 38 ቁ.1 ሐ.“ በማናቸውም ደረጃ በሚካሄዱ ምርጫ፣የመምረጥ እና የመመረጥ ፣ምርጫው ሁሉ አቀፍ፣በእኩልነት ላይ የተመሰረት እና መራጩ ፈቃዱን በነጻነት የሚገልፅበት ዋስትና የሚሰጥ መሆን አለበት፡፡”በማለት የህጎች ሁሉ የበላይ ሕግ በሆነው ሕገ መንግሰት በግልፅ ተቀምጧል፡፡

ሆኖም በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ሕገ መንግስቱን መሰረት ያደረገ ምርጫ ስለመካሄዱ አጠራጣሪለው የሚል ፓርቲ፣እንዲሁም ምርጫው ከመካሄዱ በፌት በምርጫው ሄደት ላይ ቅደመ ሁኔታ እስካልሟላለት ድረስ የታሰበው ምርጫ ነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አይደለም በማለት ከበቂ ምክንያቶች ጋር በማዛመድ ከላይ በተገለፀው የተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ አዋጅ መሰረት፣ በምርጫ ያለመሳተፍ መብት በሕግ ድጋፍ ያላው መብት ነው፡፡

ይህ መብት ከሕገ መንግሰቱ እና ከላይ በተገለፀው አዋጅ የመነጨ ሲሆን፣ ከዚህ ውጪ ያሉ ማናቸውም አሰራሮች፣ልማዳች እንዲሁም መመሪያ ይህን መብት የሚጋፉ መሆን እንደሌለባቸው የታወቀ ነው፡፡እናም ፓርቲዎች ሁሌም የፖለቲካ ምኅዳሩ ተዘግቷል፣ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄድ አልቻልንም፣መሰብሰቢያ አዳራሽ ተከለከልን……..ወዘተ እያሉ ከሚናገሩ፣ምኅዳሩ እንዲሰፋ ከገዥው ፓርቲ ጋር በመነጋገር ማስተካከል ካልተቻለ፣በጊዜ ከምርጫው ታቅበው ገዥው ፓርቲ እራሱ ደግሶ እራሱ ለብቻው ይስተናገድበት ዘንድ በመተው እውነታውን ለህዝብና ለዓለም ቁልጭ አድርጎ ማሳየት ነው፡፡እስከ መቼ በምርጫ መጭበርበር !

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !

ዲሲ የሻማ ማብራት ፕሮግራም -አንዲት ሻማ እና አንዲት ደቂቃ ለቃሊቲ እና ቂሊንጦ

$
0
0


አንዲት ሻማ እና አንዲት ደቂቃ ለቃሊቲ እና ቂሊንጦ
በአፋኙ እና አምባገነኑ የህውሃት ኢሃደግ ስርአት በሀሰት የአሸባሪነት ወንጀል ተፈርጀው በየእስር ቤቱ ተጥለው ለኢትዮጵያ ሀዝብ ፍትሃዊ ስርዓት ለማስገኘት ሲሉ መስዋትነት እየከፈሉ ላሉ የፖለቲካ እና የህሊና እስረኛ ወገኖቻችን የአጋርነት መግለጫ ወርሓዊ የሻማ ማብራት ፕሮግራም።
አገር እና ነጻነት ወዳድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ በዚህች አጭር የሻማ ማብራት ፕሮግራም ላይ በመገኘት እነዚህን ጀግና ዜጎቻችንን በምንኣብ ጉብኝት እንጠይቃቸው፣ ለአለም አቀፉ ህብረተሰብ በተለይም ለምንኖርበት የአመሪካ መንግስት እነዚህ ዜጎቻችን የነጻነት ታጋዮች እንጂ ወንጀለኞች እንዳልሆኑ ምስክርነታችንን እናሰማ።
እሁድ ዲሰምበር 7, 2014
ከምሽቱ 6 ሰዐት
ሗይት ሃውስ ፊት ለፊት

3

የማለዳ ወግ …የተዘጋውን የአረብ ሀገራት የኮንትራት ሰራተኛ አቅርቦትን ለመክፈት የወጣው ረቂቅ ! (ነቢዩ ሲራክ)

$
0
0
* ስለ ሰራተኞች መብት ጥበቃ መነሳቱ አልተዘገበም
* በተወያይ ኤጀንሲዎች በኩል ግን ረቂቁ ውዝግብ አስነስቷል
* ከዚህ ቀደም ያለ በኮንትራት ለተበተኑትስ ዜጎችስ ምን ታስቧል ?Nebiyu Sirak አዲሱን መረጃ ያገኘሁት ሃገር ቤት ከሚታተመው ከአድማስ ጋዜጣ ላይ ነው ፣ እንዲህ ይላል ” ወደ አረብ አገራት የሚሄዱ ሰራተኞች ላይ የሚደርሰውን ችግርና እንግልት ለማስቀረት በሚል ከአንድ ዓመት በላይ ተቋርጦ የቆየውን አሰራር ለማስጀመርና ለመቆጣጠር የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ውዝግብ አስነሳ፡፡ ”  … ወረድ ብለን ዝርዝር መረጃውን ስንቃኝ በዋናነት መታየት ያለበት አንኳሩ የሰራተኞች ይዞታና የመብት ጥበቃ ጉዳይ በዘገባው ላይ አልተካተተም። ይህም ይሁን ብለን ዝርዝሩን ስንቃኝ ከዚህ ቀደም በነጻ ያገኙትን ቪዛ በደላላ በየገጠር ከተሞች ሰብስበው እህቶቻችንን ከመላካቸው አስቀድሞ ፈቃድ ሲያወጡ ለመንግስት ያቀረቡት የገንዘብ መያዣ በደል ደርሶባቸው ለሚመለሱ ዜጎች ካሳ ሲከፈል አላየንም አልሰማንም ። ከሁሉም የሚያመው ሰራተኞች ሲላኩ ለሚደርስባቸው አደጋ  ኢንሹራን ሳይቀር ገንዘብ አስከፍለው የላኳቸው ቢሆንም በተበደሉበት በደል ተፈጽሞባቸው ሃገር ቤት ሲገቡ በከፈሉት ኢንሹራን ተጠቃሚ አይደረጉም። የሰራተኞችን መብት አሟልተው ስራ ለማሰማራት እንግዲህ ውል ገብተው በወሰዱት ፈቃድ ልክ ውል ሲያፈርሱ ህግ አስፈጻሚ አካላት በኩል በዝምታ የታለፉት የእኛ ስራና ሰራተኛ አገናኝ ደላላ “ኤጀንሲዎች ”  በአዲሱ ረቂቅ ያነሱት ተቃውሞ ” ቅድመ ሁኔታዎች አያሰሩንም” የሚል መሆኑን እያመመኝ አነበብኩት!  እንቀጥል …በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ሰራተኞችን የሚልኩ ኤጀንሲዎች ያሰሙት ቅሬታ የስራ ፈቃዱን ለማግኘት ” ከአንድ ሚሊዮን እስከ አምስት ሚሊዮን ብር ካፒታል ሊኖረው ይገባል ” መባሉና “ለሰራተኛው መብትና ደህንነት ዋስትና ማስከበሪያ የሚውል 100 ሺህ ዶላር ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ በዝግ ሂሳብ የማስቀመጥ ግዴታ አለበት ” መባሉ ነው ። ጋዜጣው ኤጀንሲዎች ለስራ ወደ ውጭ አገር የላኳቸውን ሰራተኞች በሚሔዱባቸው ሃገራት ላሉ ኢንባሲና ቆንስል መስሪያ ቤቶች በ15 ቀናት እንደሚያስታውቁ ይጠቁማል ።

የኤጀንሲዎች የአዞ እንባ …

ኤጀንሲዎች  ይህ መሰሉ ረቂቅ ህግ እንደማያሰራቸው እንዲያውም “በውጭ ሃገር ስራ ለማሰማራት የሚፈልጉትን ዜጎች እድል ያጠባል ፣ ህገ ወጥነትን የሚያባብስ ነው ” ሲሉ ህመሙን የመከረኞቹ ህመም በማድረግ የአዞ እንባ የማንባት አይነት ቅሬታ መሰማታቸውን በአድማስ ጋዜጣ ዘገባ ተጠቅሷል ። እንደ ጋዜጣው ዘገባ ኤጀንሲዎች ረቂቁን ህግ በወይይቱ የተቃወሙበትና ያልደገፉበት ዋንኛ ምክንያታቸው የተደነገገውን ቅድመ ሁኔታ ለማሟላት እንደሚከብድ መሆኑንም ጋዜጣው ያስረዳል ።

ዳግም እንዳናነባ …!

ከወራት በፊት ጀምሮ “ወደ አረብ ሃገራት የተዘጋው የኮንትራት ቪዛ ይከፈታል !” የሚል መረጃ በሰፊው በመሰራጨት ላይ እንዳለ በሹክሹክታ ከሰማን ወዲህ ረቂቁ ለውይይት መቅረቡን ይህው ሰማን ። ከዚሁ ጋር ባያያዝኩት የ EBC TV ዘገባ እንደ ምትመለከቱት የዜና ዘገባ ከወራት በፊት የተባበሩት ኢምሬትን የጎበኙት ፕሬዘደንት ዶር ሙላትና የኢምሬት አምባሳድር አቶ አብድልቃድር የተዘጋውን የአረብ መንገድ መቸ እንደሚከፈት ተጠይቀው ሲመልሱ  ህግ ሆነ መመሪያ እየወጣ መሆኑን ጠቁመው ነበር ። ከዚህ ጋር በማያያዝ በሰጡት መግለጫም ከአሁን ቀደም  ከአረብ ሃገራት ጋር ያልነበረው የሁለትዮሽ ስምምነት በቀጣይ መከወን እንዳለበት ገልጸውም ነበር ። ይህ መግለጫ በተነገረ ማግስት በቪዛው ንግድ ተሰማርተው ከገጠር እስከ ከተማ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ እህቶቻችን ለሳውዲ ” ገበያ”  ያቀረቡት ባለ ኤጀንሲ ደላሎች ጅዳና ሪያድ መምጣት መጀመራቸው መረጃ ቢጤ አቅርቤም ነበር  ።  አሁን በውስጥ አዋቂዎች የሰማነው ፣ የተባለው ሁሉ  እውን እየሆነ ፣ እውነቱ እየጠራ የሄደ ይመስላል  !

ከዚህ ቀደም በሁለት ሃገራት መካከል ስምምነትና በቂ ዝግጅት ሳይደረግ በሳውዲ ብቻ ከግማሽ ሚሊዮን የሚበልጥ ዜጋ  የህግ ሽፋን ህጋዊ ፈቃድ ባላቸው ኤጀንሲዎች በየገጠር ከተሞች ተግዘው በተለያዩ ከተሞች ተበትነዋል። ዛሬ በኮንትራት የመጡት ” ያሉበትን ይዞታ እንዲህ ነው” ብሎ መረጃ መስጠት ቀርቶ ፣ የትና በምን ሁኔታ እንደሚገኙ የሚያውቁ ኤጀንሲዎችም ሆነየ የመንግስት ተወካዮች የሉንም የምለው በእርግጠኝነት ነው ።  በተደጋጋሚ ከሚደርሱኝ መረጃዎች መረዳት እንደ ቻልኩት በአሁኑ ሰዓት መግቢያ መውጫው ጠፍቶባቸው ፣ በደልን እያስተናገዱ የሚንገላቱት በርካታ እህቶች በየቤቱ እንዳሉ አውቃለሁ።  በዚህ መሰሉ የተወሳሰበ ችግር ዜጎች እየተሰቃዩ ፣  መብታቸው የሚያስጠበቅ ስራ እየተሰራ በሌለበት ሁኔታ ሌላ እንባ ልናነባ የተቃረብን ይመስላል !  የኮንትራት ሰራተኞችን አበሳ ብዙ ነው፣  የሚሰራው ታስቦና ተጠንቶ ስላልሆነ ፣ መብታችን የሚያስጠበቅልን ስለጠፋ ተዋርደናል ። አሁን ድረስ በዚህ ዙሪያ ያገባናል ብለን  ስንጽፍና ስንናገረው እንደ ተቃዋሚ እየታየንም ቢሆን ግፍ ሰቆቃና ስቃዩን ሊያሰለች በሚችል ስፋትና ጥልቀት ጽፈነዋል ፣ ተናግረናል!  ሰሚ ግን የለም !

በህግ መመሪያ የተቀመጠው የመንግስት ዲፕላማቶች ቀዳሚ ስራ ባሉበት ሃገር የሚገኙ ህጋዊም ሆኑ ህገ ወጥ ዜጎችን ሰብአዊ መብት ረገጣ እንዳይደርስባቸው መከላከል ቢሆንም ይህ እተሰራበት አይደለም።  የህገ ወጦችን ቀርቶ በኮንትራት ሰራተኛና አሰሪ ስምምነት የመጡ ዜጎችን  መብት ማስከበር አልቻሉም ! የቪዛ ውል ማስፈጸሚያ ገንዘብ እየሰበሰቡ ባጸደቁት የኮንትራት የስራ ውል ላይ የተጻፉት ስምምነቶች የዜጎች  ይዞታ የመከታተልና የማስፈጸም ሃላፊነትን ሲወጡ አላየንም !እውነቱ ይህ በመሆኑ ሰብዕናችን መርከስ ይዟል ፣  ግፍ እየተፈጸብን ነው ። በዚህ ሁኔታ ረቂቁ ጸድቆና በተግባር ውሎ ዳግም እንዳናነባ ያሰጋል  !
ግልድ መሆን ያለበት ነባራዊው እውነታ …የረቂቁ ጉዳይ በእንዲህ እንዳለ ከኢትዮጵያ መንግስት አስቀድሞ ከኢትዮጵየ የኮንትራት ሰራተኞች እንዳይመጡ ያገደው የሳውዲ መንግስት እገዳውን እስካሁን አላነሳም። በዚህ ላይ መንግስት ከአረብ ሃገራት በኩል እግዱ ተነስቶ ሰራተኞች እንዲያቀርብ ጥያቄ እየቀረበለት መሆኑን ደጋግመን ሰምተናል ። ከአረቦች በኩል ግን የምንሰማው ለየቅል ነው !ወደ ረቂቁ ስንመለስ ፣  ብዙዎቻችን የሚያሳስበን በማህበራዊና ሰራተኛ ሚኒስትር ለኤጀንሲዊች ውይይት የቀረበው ረቂቅ ህግ በሰራተኞች ይዞታና መብት ጥበቃ ዙሪያ የተነሳ ጉዳይ አለመኖሩም ነው ። በአድማስ ጋዜጣ ጋዜጣ ዘገባ በማህበራዊና ሰራተኛ ሚኒስትር በቀረበው ረቂቅ ኤጀንሲዎች መወያየታቸውን ሲያስረዳ ፍቃድ ለመውሰድ የተጣለባቸውን ከፍተኛ ገንዘብ የማስያዝ ፣ ሰለሰራተኞች እድሜ የትምህርት ደረጃ ገደብ እና ሰራተኞችን በሚሄዱበት ሃገር ኢንባሲና ቆንሰል መ/ቤት በ 15 ቀን ውስጥ ከማስመዝገብ ቅድመ ሁኔታ ያለፈ አለመወያየታቸውን የቀረበው ዘገባ ያስረዳል ።

በረቂቁ ላይ ሰራተኞች ቢያንስ እስከ ስምንተኛ ክፍል በላይ የሆኑት ብቻ እንደሚያካትት ከመጠቆሙ ባለፈ ሰራተኞች ማግኘት ስላለባቸው በቂ ስልጠናና ተዛማጅ ቅድመ ዝግጅት በቀረበው ረቂቅ ቀርቦ ለውይይት አለመደረጉ ያሳስባል።  ከዚህ ቀደም ድህነትና የኑሮ ውድነቱን ተከትሎ በልጆቻቸው ህይወታቸውን ለመለወጥ የቋመጡ ወላጆች በደላሎች ቀቢጸ ተስፋ ተታልለውና የተሳሳተ የእድሜና የትምህርት መረጃና  የመጓጓዣ ሰነድ አቅርበው ከሃገር እንዳይወጡ የተሰራውን ስራ የሚከላከል ዘዴ በረቂቁ አልቀረበም።  አለም አቀፍ የሰራተኛ ህግንና ሰብአዊ መብት ማስከበሪያ ድንጋጌዎችን ባገናዘበ መልኩ ሰራተኞች ስለሚከፈላቸው ክፍያ ፣ ስለጤና ፣ ስለ እረፍት ሰአታቸው እና ስለመሳሰሉት መሰረታዊ የኮንትራት ሰራተኞች አንገብጋቢ ጥያቄዎች  ውይይት ሳይደረግበት ስለኤጀንሲዎች ፈቃድ ማግኘት ቅድመ ሁኔታ ውይይት መቅረቡ ያሳስባል። በረቂቁ ውይይት ከመደረጉ አስቀድሞ ኤጀንሲዎች  ከዚህ በፊት ስላቨጋገሯቸው ዜጎች ነባራዊ ይዞታና ሁኔታ ፣ አድራሻና ያሉበትን ሁኔታ በዝርዝር መረጃ አላቀረቡም። በላኳቸው ሰራተኞች ላይ ለተፈመውና እየተፈጸመ ላለው በደል ተጠያቂው ሳይታወቅ ስለመጭው ፈቃድ አወጣጥ ከኤጀንሲዎች ጋር በረቂቁ ዙሪያና መስፈርት ዙሪያ  መወያየቱ ጠቃሚ አይመስለኝም።

የኮንትራት ሰራተኞች ጉዳይ ሲነሳ በየአረብ ሃገራት ያሉትን ኢንባሲና ቆንስል መስሪያ ቤቶች ለዜጎች በሚሰጡት ያልተሟላ ግልጋሎትና ያልሰመረ የመብት ማስጠበቅ ይጠቀሳል። ይህ ለምን ሆነ ሲባሉ የሰራተኛና በበጀት እጥረት እንዳለባቸው አዘውትረው ይናገራሉ። በዚህ  መንገድ አሁን ድረስ ስለሚንከላወሱት የኢንባሲና የቆንስል መ/ቤቶች ረቂቁ ምን ይላል ? የሚለው እንዳለ ሆኖ በሃገር ቤት ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ዝግጅት ፣ ኃላፊነትና ተጠያቂነት በረቂቁ ውይይት አልተነሳም።

…እልፍ አእላፍ የኮንትራት ሰራተኞች አሁን ያሉበት ይዞታ በውል ሳይመረመርና ሳይታወቅ እየተንገዋለለ ባለበት ሁኔታ  የተዘጋውን ለመክፈት ሂደት ግልጥልጥ አለማለት  ያስፈራል። ከዚህ በፊት በኮንትራት የገቡት ጉዳይ ገለል አድርጎ ስለ አዲሱ ህግና መመሪያ እንነጋገር መባል ችግሩን ያገዝፈዋል እንጅ አይቀርፈውም ። ይፋ መውጣት የጀመረው ረቂቁ ህግና በዚህ ጫፍ ያለው  ዝግጅት የተዳከመ አለያም የለም የሚባል አይነት መሆኑ አሁንም የዜጎችን አበሳ በቅርብ ለምንመለከተ ውን  ዜጎች ያሳስበናል። መፍትሄው በአረብ ሃገራት ያሉትን ዜጎች ጨምሮ  የሁሉም ባለድርሻ አካላት በረቂቁ ህግ ተሳትፎ ሊያደርጉበት ይገባል። በፈለገው መንገድም ይሁን በረቂቁ ህግና መመሪያ ዙሪያ ግልጽና ጥልቅ ውይይት ካልተደረገ አሁንም ዳግም እንደምናነባ ልብ  ያለው ልብ ይበል  !

ጄሮ ያለው ይስማ  !

ቸር ያሰማል  !

ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 24 ቀን 2007 ዓም

 

መስታወት ራሱን አያይም ! ቀልዶ-አደር ክበበው ገዳና ሜሮን ጌትነት ፤ አበበ ተካ

$
0
0

Meron Getenet
abebe teka
መስታወት-ራሱን-አያይም ይህን ፅሁፍ እንድፅፍ ያነሳሳኝ በቅርቡ በሁሉም ዌብ – ሳይቶች ላይ ማለት ይቻላል ፣ የወጣ አንድ የአድናቆት ፅሁፍ ነው ። ጽሁፉ አንዲት ገጣሚትን ለማድነቅ የተፃፈ ነው ። የፅሁፉ ርእስ ሐገሬ ፤ ሕዝቤ “ ፤ ክብሬ የሚል ሲሆን በእንግሊዝኛ እንዲህ ተተርጉሟል ፤ ” “My Country, My People, My Honor” :: ይህ የአድናቆት ፅሁፍ የሚያጠነጥነው ፤ ሚሮን ጌትነት በምትባል ኢትዮጵያዊት ዘመናዊ የፊልም ተዋናይ ችሎታና በግጥሙ ታክኮ ለሃገሯ ያላት ልዩ ፍቅር ላይ ነው ። ፅሁፉ ገና ሲጀምር ነው “  —--[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—–

 

Comment

“ለመተማመን እንነጋገር!” ኢትዮጵያውያን “ከዘረኝነት ይልቅ ለሰብዓዊነት” ቅድሚያ ሰጡ!

$
0
0

 

smneበቅርቡ በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ አካባቢ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በአገራችን ውስጥ ስላለው ችግር መፍትሔ ለማምጣት ይጠቅማል በሚል በጠራው ውይይት ላይ ኢትዮጵያውያን ከአውሮጳ፣ ከአሜሪካና ከካናዳ ተጠራርተው በመምጣት በዓይነቱ ለየት ያለ ውይይት አድርገዋል፡፡ “ሰላም፣ ፍትሕ፣ ዕርቅና መከባበር የሰፈነበት ማኅበረሰብ ለመመሥረት” አንዳችን ስለሌላችን በመናገር ሳይሆን እርስበርስ ስለችግራችን መወያየት አለብን በሚል መሪ ሃሳብ ኢትዮጵያውያኑ ግልጽና በቅንነት ላይ የተመሰረተ ውይይት አካሂደዋል፡፡ “ከዘረኝነት ይልቅ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ” የመስጠት አስፈላጊነትም በስፋት ውይይት የተደረገበት ጉዳይ ነበር፡፡

በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ኤምባሲ የስብሰባው አካል እንዲሆን ለአምባሳደር ግርማ ብሩየንቅናቄው ዋና ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ የላኩ ቢሆንም ከኤምባሲው በኩል የተሰጠ ምላሽም ሆነ በውክልና በስብሰባው ላይ የተገኘ አለመኖሩ በጋዜጣዊው መግለጫ ተወስቷል፡፡ የመግለጫው ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ቀርቧል፡

 [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—–

 

 

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live