Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኢቦላ ስጋት በወር 8 ሚ. ዶላር እያጣ ነው

$
0
0

ethiopian airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ በምዕራብ አፍሪካ አገራት የተቀሰቀሰው የኢቦላ ቫይረስ በፈጠረው ስጋት ምክንያት የመንገደኞች ቁጥር በመቀነሱ፣ በወር ከ8 ሚ. ዶላር በላይ ገቢ እያጣ እንደሆነ ሮይተርስ ትናንት ዘገበ፡፡
የአየር መንገዱን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረ ማርያምን ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ ኢቦላ ለአየር መንገዱ ከየትኛውም አለማቀፍ የኢኮኖሚ ቀውስ በበለጠ በእንቅስቃሴው ላይ ተጽዕኖ የሚፈጥር ተግዳሮት ሆኖበታል፡፡
ምንም እንኳን በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው የአየር መንገዱ ዋነኛ ማዕከል፣ በኢቦላ ቫይረስ ከተጠቁት የምዕራብ አፍሪካ አገራት የረጅም ሰዓታት በረራ የሚወስድ ርቀት ላይ ቢገኝም፣ በሽታው በአየር መንገዱ ተጓዦች ቁጥር ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ መፍጠሩ አልቀረም ያሉት አቶ ተወልደ፤ ሁኔታው በመጪዎቹ ጥቂት ወራት ውስጥ እንደሚቀየርና የመንገደኞች ቁጥርም ወደነበረበት እንደሚመለስ ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል፡፡በአገራቱ የተቀሰቀሰው የኢቦላ ወረርሽኝ፣ በመላ አህጉሪቱ ከሚደረጉ በረራዎች በአብዛኞቹ ላይ ተጽዕኖ መፍጠሩንና በሽታው ለአፍሪካ አየር መንገዶች ዋነኛው ስጋት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ኢቦላ ወደ አፍሪካ አገራት በሚጓዙ መንገደኞች ላይ ስጋት መፍጠሩን የጠቀሰው ዘገባው፤ በተለይም በእስያውያን መንገደኞች ዘንድ ያለውን ፍላጎት እንዲቀንስ አድርጎታል፡፡ በዘርፉ የሚታዩ የገበያ ችግሮች እንዳሉ ሆነው፣ አየር መንገዱ የቀየሳቸውን የረጅም ጊዜ የዕድገት ዕቅዶች መተግበሩን እንደሚቀጥል ገልጸው፣ እስከ መጪው 2015 የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት፣ 3 ቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን ጨምሮ 8 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ገዝቶ በስራ ላይ እንደሚያሰማራ አስረድተዋል፡፡
በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁለት ቦይንግ 777 የጭነት አውሮፕላኖችን ለመግዛት የሚውል የ41.4 ሚሊዮን ዶላር ብድር አይኤንጂ ካፒታል ከተባለ አሜሪካ የፋይናንስ ተቋም ማግኘቱን ከትናንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
የገንዘብ ብድሩ መገኘቱና አውሮፕላኖቹ መገዛታቸው፣ በአፍሪካ ትልቁ የጭነት አየር መንገድ ሆኖ የመዝለቅ ዕቅድ ለያዘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቅምንና የአገልግሎት ጥራትን በማሳደግ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ተገልጿል፡፡

Source: Addis Admass Newspaper


በ5 ወጣቶች ተደፍራ ህይወቷ ያለፈው ሃና ላላንጎ ጉዳይ ቁጣ ቀስቅሷል

$
0
0

በአምስት ወጣቶች ተደፍራ ህይወቷ ያለፈው ታዳጊ ሃና ላላንጎ ጉዳይ ከፍተኛ ቁጣን የቀሰቀሰ ሲሆን በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀናትን ማህበራዊ ድረገፆች ላይ ድርጊቱን የፈፀሙት ግለሰቦች ተይዘው የሀገሪቱ ህግ ያስቀመጠው ከፍተኛ ቅጣት በአፋጣኝ እንዲፈረድባቸው እየተጠየቀ ነው፡፡
hanna ሃና ላላንጎ
በተለያዩ ማህበራዊ ድረገፆች፤ “ፍትህ ለሃና” የሚል ንቅናቄ የተጀመረ ሲሆን በተለይ ተጠርጣሪዎቹ ረቡዕ ህዳር 10 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው “ድርጊቱን የፈፀምነው እኛ አይደለንም፣ ለፖሊስ ድርጊቱን ፈፅመናል ብለን ቃል የሰጠነው ተገደን ነው ፈፃሚዎችን እንጠቁም” ማለታቸውን ተከትሎ የፍትህ አካላት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ የሚጠይቁ ወገኖች ተበራክተዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ አስተያየት የጠየቅናቸው የህግ አማካሪና ጠበቃ አቶ ጳውሎስ ተሰማ እንዳብራሩልን፤ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ በአንቀፅ 620 ንኡስ ቁጥር 1 መሰረት፤ “በግብረስጋ ግንኙነት ነፃነት እና ንፅህና ላይ የሚፈፀም ወንጀሎች” ብሎ በአስገድዶ መድፈር ርእስ ስር “ማንም ሰው ሀይል በመጠቀም ወይም በብርቱ ብቻ የሚፈፀም ድርጊት ወይም ህሊናዋን እንድትስት በማድረግ ወይም በማናቸውም መንገድ እራሷን መከላከል እንዳትችል በማድረግ ከጋብቻ ውጪ አስገድዶ ከአንዲት ሴት ጋር ግብረ ስጋ ግንኙነት የፈፀመ እንደሆነ ከ5 ዓመት እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ይቀጣል” የሚል ሲሆን በአንቀፅ 620 በንዑስ ቁጥር 2 ላይ እድሜዋ 18 ዓመት ባልሞላት ሴት ልጅ ላይ የአስገድዶ መድፈር በሚፈፀምበት ጊዜ የግል ተበዳይ በተከሳሹ ቁጥጥር ስር በምትገኝበት ወይም በሱ ጥገኛ በሆነች ጊዜ ቅጣቱ ከ5 ዓመት እስከ 20 ዓመት ድረስ ይሆናል፡፡
ታዳጊዋን ለስራ የተሰማሩ መስለው ሲንቀሳቀሱ በታክሲው ተሳፍራ በቁጥጥራቸው ስር እንድትሆን በማድረግ ወንጀሉን በህብረት የፈፀሙባት በመሆኑ ቅጣቱ ከ5 ዓመት እስከ 20 አመት ይደርሳል፡፡ አስገድዶ መድፈሩ በተበዳይ ላይ የሞት አደጋ ያስከተለ እንደሆነ ከላይ በጠቀስነው የወንጀለኛ መቅጫ ህግ፤ ቅጣቱ እድሜ ልክ እስራት ይሆናል፤” ያሉት ጠበቃው፤ “በታዳጊዋ ላይ የተፈፀመው ወንጀል ከአንድ በላይ በመሆን ጭካኔ በተሞላ ሁኔታ በቁጥጥራቸው ስር በምትገኘው ለአቅመ አዳም ያልደረሰች ልጅ ላይ በመሆኑ በዕድሜ ልክ እስራት ይቀጣሉ” ብለዋል፡፡ ተደራራቢ ቅጣቶች አቃቤ ህግ ከከፈተ ቅጣቱን ሊያከብደው ይችላል፤ ነገር ግን የአስገድዶ መድፈር ህግ ላይ ከእድሜ ልክ እስራት በላይ የተቀመጠ ነገር የለም ሲሉ አስተያታቸውን ሰጥተዋል፡፡
በሌላ በኩል የኢፌዲሪ ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ በሰጡት መግለጫ፤ ድርጊቱን የፈፀሙትን ግለሰቦች ለፍርድ ለማቅረብ ጠንክሮ እንደሚሰራ አስታውቆ፤ በሰብአዊ ፍጡር ላይ ኢ-ሰብአዊ ጥፋት የሚፈፅሙ የሰው አራዊቶች ከህግ በላይ አይሆኑም ብሏል፡፡
አየር ጤና በሚገኘው ታይምስ ኢንተርናሽናል ትምህርተ ቤት የ10ኛ ክፍል ተማሪ የነበረችው የ17 ዓመት ታዳጊ ሀና ላላንጎ፤ አየር ጤና በተለምዶ ሳሚ ካፌ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ በሚኒባስ ተሳፍራ ወደ ጦር ኃይሎች መስመር በመሄድ ላይ እንዳለች በሚኒባሱ ውስጥ በነበሩ አምስት ወንዶች ታፍና ተወስዳ፣ በተፈፀመባት አስገድዶ መድፈር በደረሰባት ከፍተኛ ጉዳት በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ህክምና በመከታተል ላይ ሳለች ህይወቷ ማለፉ የሚታወስ ሲሆን ድርጊቱን ፈፅመዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበው ድርጊቱን አልፈፀምንም ብለው ክደዋል፡፡ ፍ/ቤትም ጉዳዩን ለህዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡

Source: Addis Admass Newspaper

የወያኔ ምርጫ –ለእርግጫ። (ሥርጉተ ሥላሴ )

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 21.11.2014 /ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ/

ጭል ጭል ስትል የነበረችው የብዕር ጧፍ ተከረቸመች – ለወያኔ የምርጫ እርግጫ ማጫ መመቻ በመሆን ለካቴና – ተሰጠች።

ሥልጠናው እርግጫ፤ መንገዱ ውንብድና፤ መንፈሱ ፍጥጫ የወያኔ ተፈጥሮ ይሄው ነው። ሥርዓትና ወያኔ ተያይተውም አያውቁም። ይልቁንም ሥርዓተ – አልበኝነት የዋኘበትና የናኘበት  መሆኑን ከተፈጠረበት ሀገርን የማክስል ተልዕኮው ቀን ጀምሮ ያሉት ሁኔታዎች አንድ በአንድ ቢፈተሹ ፍሬ ነገሩን ማግኘት ይቻላል።

2007 electionወዬኔ በተፈጥሮው የአውሬነት ሰብዕና የተለበሰ ነው። አውሬነት ደግሞ ጸረ ሰው በመሆኑ በሰበነክ ጉዳዮች ላይ የሚወስዳቸው መጠን ያለፈ የጭካኔ እርምጃዎች እራሳቸው ቆመው ይመሰክሩበታል። እርግጥ ወያኔ በተለዋዋጭ ባህሪው አጥፊ ፍላጎቱን ለማስፈጸም አስችሎታል። በማጭበርበር – በማምታታት ደጉን የኢትዮጵያ ህዝብ አጃቢ በማደረግ ለሥልጣን መብቃቱ ብቻ ሳይሆን፣ የሚገርመው ህዝባዊ የእንቢተኝነት ሞገዳማ ነበልባሉ ዘመን መራዘሙ ምክንያቱ ቅጥፈቱና እራሱን ገልጦ ለማሳዬት ድፍረት የሚያንሰው በመሆኑ ነው። ወያኔ በክንብንብ ኖሮ በክንብንብ ያልፋል። አልማጭ!

ቀባ አድርጎ አብልጭልጮ አንድ ህዝበ ጠቀም ዬሚመሰል ግን ገዳይ ፖሊሲ ያወጣል። ወገን ላይ ላዩን ብቻ አይቶ የተሻለ – የበለጠ – የሚሆን ነገር ተገኘ ብሎ በፍቅር ከአዲሱ የሽፍታ ቅብ ፖሊሲ ጋር ደፋ ቀና ሲል፣ ቀስ እያለ እዬሸረሸረ ወደ አቀደውና ወደ አለመው ላጥ ወደ አለው ገደል ይዞ መሄድ ብቻ ሳይሆን፤ ተስፋን ከነስብዕና ቅጥቅጥ አድርጎ ይቀጣበታል። “ወንዝ ሲወስድ እያሳሳቀ” ይበል የለ – እንደዛ ነው ነገሩ።

ወያኔ በሥልጣን መባቻው ነፃ ፕሬስ አንደ ጉድ ፈቀደ። ማህሌት፤  አዕምሮ፤ ሙዳይ፤ ጦቢያ፤ አፍሪካ ቀንድ፤ ኢትዮጲስ፤ ሳታናው  ወዘተ … መጽሄቱም ጋዜጣውም በገፍ መታተም ጀመሩ። ነፃነት የጠማው ብዕር ስለ ነፃነት፤ ስለመናገር መብት፤ ስለ የህግ የበላይነት፤ ስለ ኢትዮጵያዊነት፤ ስለ አብሮነት፤ ስለ ፍቅር የሚገባውን ያህል ቀን ከሌት – ማሰኑ። … ህዝቡም የራበውን መተንፈሻ ስላገኘ በሽሚያ፤ በቋሚ ደንበኝነት ጸሐፍትን አበረታታ – አደነቀ – ሃቅንና እውነትን ከበከበ … ግን ቀጠለ ….? እእ ….

“የፕሬስ ነፃነት በኢትዮጵያ” የወያኔ የመቅጫ መንገዱ ማሟሻ ነበር። ነፍሱን ይማረውና በጋዜጠኛ ተፈራ አስማረ ግንባር ቀደምትን ወህኒ ቤቶች በመጽሄትና በጋዜጣ አዘጋጆች ተጨናነቁ። ፍርድ ቤቶችም ሚዛንን ገልብጠው የሚሰቅሉበትን ሁኔታ ወያኔ አመቻችቶ አደራጀላቸው። ከዚህ በኋላ ዒላማውን ጎሰኛው ወያኔ አስተካክሎ እስኪበቃው ድረስ ነጻውን ፕሬስ ወቃው። የመናገር፤ የመጻፍ፤ ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ ሆነ የማንበብን የለመለመ ተስፋንም ገንዞ በድፍረት ቀበረው። ጭላጭሏንም ሶሞኑን ዳፍንት አለበሰው። ደፋሩ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ቀርቶት ነበር እሱንም ለእግር – ብረት፤ ከህዝብ እውነተኛ ብሶት ተነስታ ጭብጥን – በጭብጥ አዋዳ ለመንፈሳችን ሁነኛ ስንቅ የነበረቸው የተመስገን ትእግስቱ /ደሳለኝ/ ብእር – የካቴና ስንቅ ሆነች። ይህቺ የእርግጫ ምርጫ ስትመጣ ጉድጓድ ውስጥ ተቀብሮ የቆዬ ውሻ ያደርገዋል። ደም – ደምም ይሸተዋል – አረሙ።

ይህን ለምሳሌ አነሳሁ እንጂ ወያኔ አቅዶ የሚወጣቸው ማናቸውም ትልሞች ሁሉ የተከደነ ወይንም የተሸፈነ የበቀል ተልዕኮ አሽኮኮ አድርገው ነው የሚወጡት። አንዷ ቃል ወይንም ሐረግ ለምለም ዝግን ትመስላለች። ግን በመርዝ የተቀመመች የመሞቻ እንክብል ናት። አረሙ ወያኔ የተነሳበት ሆነ ያለመው ቂምና በቀልን ሥልጣን ይዞ እንዴት ተግባር ላይ ማወል እንደሚችል ነበር። በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ከእጁ የገባ ማናቸውም ፍጡር የማናቸውም ዓይነት ሰቆቃ መፈተኛ ነው የሚሆነው። ይህን በግለሰብ ደረጃ አይተን ወደ ሀገራዊ ጉዳይ ስናመጣው ስንት በደልና መከራ ሀገራችን ኢትዮጵያ እንደ ተሸከመች መገመት ይቻላል።

እኛ ደግሞ ነገረ ሥራችን ግልጥና ቀጥተኛ ስለሆን የምንፈልገውን፤ ያስብነውን፤ ውስጣችን የሚነግረንን፤ ያቀድነውን በነፃው ሚዲያ በሉት በመጸሐፍ እናወጣለታልን። ይህ እሱ ቆልፎ ላስቀመጠው ሸሩ ድውለቱ ነው። በቀጣዩ ጊዜያት ወራት ሆነ አመታት በተገባው ተሰናድቶ አዲስ መሰል ግን በቀልን ያረገዘ ደንብና ህግ ያሰናዳበታል። ወይንም ስስ ነው በተባለው ቦታ እዬሰበረ የሚያኖር አዲስ ህግ ያረቅበታል …. ውድ የፁሁፌ ታዳሚዎች ታስታውሱ ከሆነ የሳውዲው የወገን ሰቆቃ ወያኔ የተጋለጠበት፤ ዬኢትዮጵውያን ቁጣ የነደደበት ወቅት ነበር። ታዲያላችሁ ወያኔ ቀዳዳውን ለብዶ የሸፈነበት መሳሪያው የተከበሩ ዶር/ ካሳ ከበደ ከኢሳት ጋር በነበራቸው ቆይታ በሰጡት የበሰለ በተመክሮ የፀደቀ ትንተና ነበር። ዝሎ የነበረው የወያኔ መንፈስ ተነቃቅቶ ጣዖት አምላኪዎቹ ከበሯቸውን እንዲያንኳኩ ያገዛቸው።

…. ከዛ ግልብ የታይታ ተግባር በኋላ ለወገኖቻችን ምን ተደረገ? ምንም። ሁሉን ነገር ስታዩት የነፈሰበት ጉድ ነው። መጣፍያ ነገር። ለነገሩ ማጣፊያው ለትንፋሽ ስለሚያጥረው ነው። ወያኔ የእኔ የሚለው ብቃት እኮ የለውም። የኢሠፓ ካድሬዎች ናቸው ነፍስ የዘሩበት። …. ስለምን ይህን ወንጀል እንደሚፈጽሙ አይገባኝም። አዎን ወንጀል ነው። የመጀመሪያው በሁለት ቢላዋ መብላት ሲሆን ሁለተኛ ደግሞ እንዲህ ላለ ርኩም – እርጉም ሥርዓት ጧፍ አብርቶ ማሽሞንሞናቸው ነው። ልምድና ተመክሯቸውን በገፍ መለገሳቸው … ታሪክን የማቃጠል ያህል የሀገር በደል ነው። ተደናብሮ እንዲወድቅ ነበር ማደረግ የነበረባቸው። ያውም እኮ እነሱም ቢሆን እንደ አሮጌ አካፋና ዶማ ከተጠቀመ በኋላ …. እህል ውሃቸው እልቅ —-

አሁን ይሄ ምርጫ የሚባለው ነገር ወገኖቻችን በገፍ ወደ እስር ቤት የሚወረወሩበት፤ ሴት ልጆች በግፍ የሚደፈሩበት፤ ደጁ ሜዳው፤ ዱር ገደሉ በፍርሃትና በስጋት የሚዋጥበት፤ መተንፈሻ ባንቧዎች ሁሉ የሚዘጉበት ህዝብን በነቂስ የሚያሳድድበት ዘመቻዊ ትልሙ ነው። እንዲሁም ወያኔ ወዳጅና ጠላቱን የሚለይበትና በጠላቶቹ ወይንም ፊት – ለፊት በወጡት ተቀናቃኞቹ ላይ ቂምን ቋጥሮ አጋጣሚ እዬፈለገ የሚያድንበት መረቡ ነው። ከዚህም በላይ በተነጠላዊ ህይወትም ውስጥ በሚያሰማራቸው ሰላዮቹ አማካኝነት የቤት – ለቤት ውጥረቱን አጠንክሮ ሰላም የለሽ ኑሮ ህዝባችን እንዲኖረው የሚያደርግበት እጅግ የረቀቀ የበደል ጋሜና ቁንጮው ወይንም በደልን የሚያስጌጥበት ወቅቱ ነው። የወያኔ ምርጫ እርግጫን አስልቶ – ወገኖቻችን በጥርስ የሚገበቡት ተለይተው ከላይ እሰከ ታች ዝርዝራቸው ተይዘው በዓይነ ቁራኛ የሚጠበቁበት የመጠራቅቅ ወቅት ነው። …. በአፈና፣ በማሳደድ፣ መርዝ በመስጠት፣ ከሥራ በማስለቀቅ፣ ከእድገት በማገድ፣ ከቦታ በማዛወር ማናቸውም አለ የተበለ የቂም እርምጃውን የሚወስድበት የማጥቂያ፤ አቅዶ የሚፈጽመው አሳቻ * መንገዱ ነው። ለዛውም ከእርግጫ – ከፍጥጫ  – ከአውሬነት ስብእናው ጋር …..

ስለዚህ ይህን አራት አመት እዬቆጠረ በሚያመጣው የማሳደድ ዘመቻ መደገፍ – መሳተፍ – ማሟሟቅ – ተስፋ ማደረግ - አጀንዳ ማድረግ – መንፈስን መስጠት – መስዋዕትን መክፈል – መዋለ ንዋይ ማፍሰስ ያስፈልጋዋልን? ….. ሂደቱ “ላም አለኝ በሰማይ ወተቷን የማለይ” ሥነ ውበታዊ ፈሊጥ በእውን ተግባራዊ የሚሆንበት ከመሆኑ በተጨማሪ …. በወገኖቻችን ላይ በስተጀርባ የሚፈጸው ድርብ ድርብርብ ሰቆቃ ደግሞ ሚዛን ከቶውም ሊወጣለት አይችልም። ዛቪያው ይሸከረከራል ወገን ይታረስበታል – በግፍ።

ስለዚህ የተገፋ ወገን፣ የከፋው ወገን፣ የተከ ወገን፣ የተራበ ወገን – ባይታዋርነት በሀገሩ ላይ ተፈርዶበታል፤ በሌላ በኩልም ሳይፈልግ ወይንም ሳይመኘው የተሰደደው ወገንም ቢሆን ሃገሩ በዓይኑ እንደ ዞረች – እዬቀረ ነው። ስለሆነም ወገን ምን ማደርግ አለበት? ነው የጹሁፉ መሰረታዊ አናት። የአጭበርባሪን – የእርግጫ ምርጫ ለእሱ የሚፈይደው አንዳችም ነገር አንደሌለ ካለፉት ምርጫዎች በስማ በለው ሳይሆን በህይወት ተኖረበት። አሁን የምርጫው ውጤት በድርጅታዊ ሥራ ድልድል ተደርጎበታል። ለሁሉም ቦታ በውስጥ ታዋቂነት ሰው ተመድቦበታል። ለምስል ነው ዬምርጫ እርግጫ ዳንኪራ የተሰናዳው። ወያኔ የሚመራበት ርዕዮት የሶሻሊዝም አናርኪዝምን ነው። ስለዚህ ሰፊው  ዬኢትዮጵያ ህዝብ የመከራው ገመድ የሚበጥስበትን ዘላቂ ተከታታይ ተግባር መከወን ይኖርበታል።

መበታታኑ ሆነ ተነጠላዊ ትግል ሀገር ቤት ላይ የሚያወጣ መንገድ አይደለም። የወልን ችግር በወል ለመወጣት በጋራ መነሳትን ይጠይቃል። ሰራተኛ፤ ጋዜጠኛ፤ ጸሐፊ፤ የእምነት ማህበር ምእመናን፤ ነጋዴ፤ ተማሪ በዬጊዜው ብሶታቸውን በአንድም በሌላም መንገድ ይገልፃሉ። …. አንድ ነጣላዊ ፍላጎትን ብቻ አንግበው። ነገር ግን ጠቃሚው ነገር ይህን ተናጠላዊ ፍላጎት ወደ አንድ ማዕከል አምጥቶ ህዝባዊ አልገዛም ባይነትን በተከታታይ  አደባባይ ማዋል ብቻ ነው መፍትሄ ሊሆን የሚችለው። የአንድ አካል ብቻ ሩጫ – ትንሽ ነጥብ፤ የሁሉም አካል የጋራ ሩጫ ግን ሙሉ ተስፋን በእጅ ያስገባል። ጥላቻው ሥራዓቱና የሚተዳደርባቸው ህግጋት ብቻ በመሆናቸው ይህን በበሰለ አምሮ አመዛዝኖ ሥርዓቱን እስከነመመሪያው እንዲወገድ የማደረግ ዘመቻ ነው ለነፃነት ትግሉ ስንቅም ትጥቅም ሊሆን የሚገባው። ግለሰብ ቢወርድ ግለሰብ ይተካል። ሄሮድስ መለስ ዜናዊ አለፉ … ግን ሥርዓቱ አለ። … ለዛው ኢትዮጵያዊነትን እዬነቀለ።  የአቶ በረከት ሆነ የአቦይ ህልፈት ወይንም የአቶ ቴወድሮስ አድሃኖም የአውሮፕላን አደጋ ደርሶባቸው ቢያልፉ እንኳን መፍትሄ አይሆንም። መፍትሄው ጠላታችን የሆነው የወያኔ ማንፌስቶ ከጥቅም ውጪ የሚያደርግ ሥርአት መፍጠር ነው። ለዚህ ደግሞ ፍላጎትን ወደ አንድ አቅጣጫ ማምጣት መሰረታዊ ጉዳይ ነው።

ይህ ደግሞ ይቻላል “ሃምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ ለሃምሳ ሰው ጌጡ” መከራውን – ስቃዩን – ፍዳውን – አታካች ኑሮውን ህዝብ አዳምጦ ለምላሹ እያንዳንዱ በነፍስ – ወከፍ የሚሳተፍበት “ሰላማዊ አመጽ” በመንፈስ ማህጸን ሲነግሥ የቅጽበት እንቅስቃሴ  ዬእልፍኝ ባለቤትነትን ያውጃል። ዛሬ እንዲህ ተፈሪ የሆነው የወያኔ የእርግጫ ህግ ህዝባዊ አመጽ ሲፈናዳ ህጉ እራሱ መሸሸጊያ ትንሽ ቁጥቋጦ ብቻ ነው የሚፈልገው። መጓጓት መልካም ቢሆንም ጉጉትን ማናር ግን የተገባ አይደለም። የጉጉት ህያውነትን በእጅ ያለ ብቃት ብቻ ነው የሚወስነው። የበቃ ተግባር – የበቃ ጉጉትን ያሳካል። ቤት ውስጥም ሆኖ እኮ ጸጥ ብሎ ማመጽ ይቻላል።

ምርጫውን ወያኔ የሚካሂደው ሳይወድ የተቀበላቸውን አሻንጉሊቱን ጠ/ሚር አውርዶ የራሱን ደም የሆኑትን አቶ ቴወድሮስ አዳህኖምን ለማጸደቅ ነው። ያው ከላይ የጠቃቀስኩላችሁ የቂም ማወራረጃው ሁነቶች እንደተጠበቁ ሆነው። ስለሆነም የነጻነት ትግሉ የእሱን የጢባጢቦ ግርድፍ ተውኔቱን ለራሱ አሸክሞ፤ ቀጣይ ሥራን መስራት ያስፈልጋዋል። “የእርግጫን ምርጫ” አይደለም ለ2007 ተሳክቶለት በቀጣዩም 2011 ክፍለ ጊዜ ቢያመጣው ከህሊና መሰረዝ ያስፈጋል። “የእርግጫ ምርጫ” ለእኛ በዕድ ራዕይ ነውና። እስከ እርግጫ ምርጫው መባቻ ሆነ እስከ ምርጫው ድንፋታ ስክነት ከዚያም ባለፈ ወደ ነፃነታችን ሊያሸጋግረን የሚችለው ድልድዩ ተጎሳቅሎ ሊቆይ ይችላል። ይህን ግምት ውስጥ ማስገባት ይገባናል። … ድሉ ዛሬ ወይንም ነገ ላይሆን መቻሉ የነፃነት ትግል ባህሪ ነው። ትግል ረጅሙን የጨለማ ጉዞ ተጋፍጦ ነው ብርሃን ማግኘት የሚቻለው … ተፈጥሮው ይሄው ነው። አታካች – አቅምን ፈታሽ ነው – የነፃነት ትግል። ትንፋሹ ግን ጠንካራና የማይሞት ነው።

አሁን ባለፈው አመት ሰፊ የማደራጀት የተቃውሞ ተግባራት ሀገር ቤት ተከውነዋል። እነዛ መልካም ናቸው። ያደጉና የሰለጠኑም ነበሩ። አሁን ደግሞ ትግሉን ከፍ በማደረግ “ወያኔ በቃህን! ከሥልጣን ውረድ” የሚል መንፈስን መፍጠር – ማደራጀትና መምራት ያስፈልጋል። ምርጫው የእኛ አይደለም። ወደፊትም ወያኔ እስከ አለ ድረስ የእኛ ሊሆን ከቶውንም አይችልም። የእኛ ምርጫን የምንጠብቀው እራሳችን አምጠን በምንወልደው ነፃነት ብቻ ነው። ነፃነቱን በመንፈሱ የጸነሰ የነፃነት አርበኛ የጊዜው መርዘም ወይንም የሂደቱ አድካሚነት ወይንም የመንገዱ ኩረታማናት ወይንም የተስፋው ሩቅነት ምኑም አይደለም። እንዲውም ለነፃነት ትግል የጊዜ መስፈርት ግጥሙ አይደለም።

ስለሆነም ለዘላቂ ፍላጎት ዘላቂ ጽናት በእጅጉ ያስፈልጋል። ጽናቱን ወያኔ በሰላዮቹ አማካኝነት ብል አስብልቶ ተስፋ ቆራጭነት እንዲነግሥ ሊያደርግ ይችላል። ቀሪዎቹ ጽናት ያላቸው ሃይላቸውን ለወያኔ ግብር ሳያውሉ በሥልጡን ስልታማ አመራር ትግላቸውን ቆርጠው መቀጠል ይኖርባቸዋል። ወገኖቼ አንድ ሰው ብዙ ነው። ይህን አንዲት ጠንካራ ሴት እጅግ ዝቅ ካለ ማህበረሰብ ተፈጥራ ለተነሳችበት ዓላማ አይደለም ሀገሯን አህጉሩን እንዴት እንደ ፈወሰች ጹሑፉን ስጨርስ አስነብባችኋለሁ። እንኳንስ ከአንድ በላይ ሆነን ….። የነፃነት ትግሉ ቤተስብ ሲሰበሰብ አዳራሹ ሞላ አልሞላ ጭንቀታችን ሊሆን አይገባም። ከተሰብሳቢዎቹ በአንዱ መንፈስ ውስጥ ያለው ቅዱስ ሃይል አቅሙ ብሩክ ሊሆን ይችላል። አድህኖት ሊሆን ይችላል። ብርሃን ሊሆን ይችላል። ስናሸንፍ ደግሞ አጃቢያችን እልፍ ነው የሚሆነው …

ትግላችን የመምረጥ መብት ሀገር ቤት ብቻ ሳይሆን፤ ውጪ ሀገር ለሚኖሩ ኢትዮጵውያን በዬሚኖሩበት ሀገር ድምጻችን የመስጠት መብታችን አስኪረጋገጥ ድረስ መድከም ይኖርብናል። ይህ ሊሆን የሚችለው ግን የጎሳ አስተዳደር ከነማኒፌስቶው ግብዕተ – መሬቱ በህዝብ ህብረ አመጽ ሲደረመስ ብቻ ይሆናል። እንችላለን! ከቆረጥን! አሁንም እንደ ገና ሃይላችን አቅማችን ገንብተን ከብረት ቁርጥራጭ በተሰራ ዬመንፈሰ ጥንካሬ ትግላችን ከመራነው ነገን እናበራለን …. እኛም እንበራለን – በመሬታችን ላይ።

የማከብራችሁ ደሞቼ የሀገሬ ልጆች የነፃነት ትግሉን ፍላጎት እናሳድገው። ወያኔን ተወዳድሮ በምርጫ ማሸነፍ እንደማይሆን እናውቀዋለን። ከጎሳ ሥርዓት ተፈጥሮ ስንነሳ የምናገኘው አምክንዮ ይሄው ነውና። ነገር ግን ወያኔን ከሥሩ ለመንቀል የምንሰራቸው የመንፈስ ሥራዎች በራሳቸው ለድል ያበቁናል። የወያኔ ሥርዓት እሾኃማ ብቻ ሳይሆን ለትውልዱ መርዛማ ነው። ስለሆነም መወገድ አለበት። ሰሞኑን  ዛሬም ባዬሁት ሪፖርት በትንታጎቹ በነአቶ ሃብታሙ አያሌው ክስና በውዴ በአብርሽ የክስ ጭብጥን በሚመለከት እንዴት አድርጎ እንደ በለተው አይታችኋል። ውዴን አብርሽን ወደ ማነው ጠጋ ያደረገው ወደ ደምሂት አያችሁት ይህን ፍልስፍና … እባካችሁ የኔዎቹ ጊዜ ወስዳችሁ መርምሩት። … በኛ መንፈስ እንዴት ቢላዋውን አስልቶ ሽንሸና ለመፈጸም እንደ ተሰናዳ። እንዲህ ነው ሃሳባችነን ህሊናችንን ወላዊ ጥንካሪያችን ስንጥቅጥቅ የሚያደርገው። ስለዚህ ወያኔ ለኢትዮጵያዊነት ህልውና አጥፊ ዘር ነውና መወገድ አለበት። ወያኔ አረማሞ ዘር * ነው።

እርገት ይሁን – አንድን ነገር ማብሰል ያለብን ይመስለኛል። ይሄ “ወያኔ አልቆላታል፤ ባዶ ቀርቷል” በማለት የምናቃልለው ነገር መቆም ያለበት ይመስለኛል። ጠላትን ማቃለል የተገባ አይደለም። ባቃለልነው ቁጥር ሃይላችን ይሰንፋል። ጉልበታችን ይዝላል። ለነፃነት ትግሉ ልንሰጥ ያሰብነው ጉልበትም በተቀናሽ እሳቤ ይሆናል። ወገኖቼ – የኔዎቹ ወያኔ ሥልጣን ላይ ያለ፣ በተሟላ ሎጅክስቲክ የተደገፈ፤ በውጭ ሃይሎች ሙሉ ድጋፍ የሚደረግለት መሆኑን መዘንጋት የለብንም። ከዚህም በላይ የጎጥ ድርጅት መሆኑ ደግሞ ሌላው ስብጥር ዕዳ ነው። …. ጎጡ በጋብቻ – በዝምድና – የተሳሰረ ነው። ስለዚህ ይሄን ጥሶ ለመውጣት የነፃነት ትግሉ የበለጠ ሃይልና ጥንካሬ ይጠይቀዋል። ጊዜም።  የፍላጎታችን መዳረሻ መዝግዬትም ምክንያቱ ይሄው ነው። ስለሆነም ሳያጋኑ ወይንም ሳያንኳስሱ …. ሚዛኑን በጠበቀ …. ግንዛቤ መጓዙ ጠቃሚ ይመስለኛል። ኑሩልኝ የኔዎቹ። የትናንት 20.11.2014 Tsegaye Radio የወግ ገበታ ካሰኛችሁ አርኬቡ ላይ አለ። ገባ ብላችሁ ኮምኩሙ … መሸቢያ – ሸበላ ሰንበት።

  • አረማሞ … ዘሩ ያፈራል። የሚያፈራው ግን ተፈጥሮ የማያውቀው የጥቁር ቀለም አመድ ነው። እርግጥ ሲያድግ ልክ እንደማናኛውም ባህር ማሽላ፤ ወይንም ስንዴ ቡቃያ ተስተካክሎ ነው። እሸቱን ከተሸፈነበት ስተግልጡት ግን የላመ ጥቁር የተቃጠለ አመድ ነው። ወያኔም እንደ እኛው ሰው ሆኖ የተፈጠረ ግን በተፈጥሮ የተበደለ የተቃጠለ አፈር ነው
  • አሳቻ – በግልጽ የማይታይ አሳሳች ስውር መንገድ፤
  • ማሳሰቢያ በትህትና … ለተስፋ መተያያ የአቶ ዮፍታሄ ክፍል አንድ – ሁለት – ሶስት እና ተከታይ ጹሑፎችን ደግመን ደጋግምን እናንበብው። እጅግ ጠቃሚ ጹሑፍ ነው ከምለው ጭብጡን “የኢትዮጵያዊነት ማኒፌስቶ” ብለው ይቀለኛል። “ሰንደቃችን” ነው። በድምጽም እኔ በተከታታይ እሰራዋለሁ።

 

ፅናትን የሰነቀ የነፃነት አርበኛ ድሉን ያያል!

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

የማለዳ ወግ …የሃና አባት አቶ ላለንጎ ሃይሶ አና እናቷ ወሮ ትርፊ ተናገሩ! ያማል ፣ ያማል ፣ ያማል …ይህም ያማል !

$
0
0

hanna ሃና ላላንጎነቢዩ ሲራክ
እህት ሃና በሰው አራዊቶች ለአምስት ተከታታይ ቀናት ተደፍራ ወድቃ ያገኟት አባት ልጃቸው ህክምና ታገኝ ዘንድ ከሆስፒታል ሆስፒታል ስለተንከራተቱበት ፣ የህክምና እርዳታ ስለተነፈጉበት አሳዛኝ ሂደት ሀገር ቤት በሚተላለፈው ኤፍ ኤም ራዲዮ ተናግረዋል ። አባት ሲናገሩ ለሃና ህክምና ማድረግ ያልቻሉት የመንግስት ህክምና ተቋማት ሳያንስ ፖሊስ ጉዳዩን እንዲመረምር በልመና ካሳኩ በኋላ ህክምና ማግኘት ባለመቻላቸው የሚረዳቸው አጥተው ተጎጅ ልጃቸውን ይዘው ወደ ቤታቸው ወስደው ስላሳደሩበት እንግልት ሰምተናል ፣ ይህም ያማል: (

እንደ አባት አቶ ላላንጎ ገለጻ ልጃቸው እህት ሃና ከጋንዲ ጥቁር አንበሳ ከጥቁር አንበሳ ዘውዲቱ ግልጋሎት ተነፍገው ተንከራተዋል ። ወደ መጨረሻም በዘውዲቱ ሆስፒታል አልጋ ተሰጥቷን መታከም መጀመሯንና በህክምና እያለች የምስክርነት ቃሏን በደል አድራሽ ያለቻቸውን ሶስቱ በፖሊስ ተይዘው ቀርበው ለይታ ማሳየቷን አባት ተናግረዋል ። ሃና በመጨረሻ ሰአቷ ከምስክርነት አልፎ በኑዛዜዋ በጉዳዩ የሉበትም ያለቻቸው እንዲለቀቁ መናገሯንና ከወንጀሉ ጋር ግንኙነት አላት ያለቻትን ጓደኛዋን ፖሊስ ” በቂ መረጃ የለም!” በሚል እንደለቀቃት ሲናገሩ ይህም ከሃዘን በላይ ሃዘን እንደጨመረባቸው ቅሬታቸውን ተናግረዋል !

ምስኪኗ እናት ወሮ ትርፊ …

የሃና እናት ወሮ ትርፊ የልጃቸው የሃናን ስቃይ መመልከታቸውን ፣ በማደንዘዣ መቃጠል መንገብገቡ በረድ ሲልላት ነፍስ እየገዛች የሆነው ሁሉ መናገሯን እያነቡ እያነቡ ከአድማስ ራዲዮ ጋር የተናገሩት እናት የሃናን በደል መደበቁ ትድናለዕ የሚል ተስፋ ስለነበራቸው እንደነበር እያነቡ ልብን በሃዘን በሚሰብር ስሜት ተናግረዋል … በመጨረሻም ባስተላለፉት መልዕክት ” በሃና ግፉ ይብቃ ሲሉ ባስተላለፉት መልዕክት እንዲህ ” … እኔ ያለኝ ነገር በሃና ሁሉም ነገር እንዲቀር ፣ ለምን አሁንም ትውልዱ አየተበላ ነው ፣ ህጻን እየተበላ ነው ፣ የህጻናት መብት እንዲከበር ፣ ትክክለኛ ፍርድ እንዲሰጥ ነው የምፈልገው ፣ ልጀ አትመጣልኝም በቃ ምን አደርጋለሁ? አሁንም እንደቀጠለ ነው … ለእኔ እንደሁ አትመጣልኝም ….ትክክለኛ ፍርድ እንዲሰጥ ነው የማስተላልፈው! ” የዚህች እናት ህመም ህመማችን ነው ! መልዕክታቸው መልዕክታችን ነው ! ያም ሆኖ ይህም ያማል ፣ ያማል ፣ ያማል !

አዎ በርካታ ሃናዎች በአረብ ሃገራት መካከል የሁለትዮሽ ውል ባልተደረገበት ሁኔታ ለኮንትራት ስራ ወዳለሁበት ጃገር ተልከው ግፍ ተፈጽሞባቸው አይቻለሁ ፣ ሰምቻለሁ! ምንዱባኑ ታዳጊዎች እድሜያቸውን ቆልለው በመጡ በርካታ እህቶች ባልጠነከረ ለጋ ገላቸው ተጎድቷል። ግፍን አስተናግደውየተረፉት ተርፈው በመንግስት ወኪሎች አማካኝነት ሱሸኙ በቂ ህክምናና ፍትህ አግኝተው አላየንም። ይህ ሆነና እውነቱ ግፉአኑ ተገፍተው ወደ ድሃ ጎጇቸው ለመሸኘታቸው እማኝ ነኝ ። የእኒያ እናቶች ድምጽ እንደ ሃና እናት ባንሰማውም የሰቆቃ ህይወታቸውን ፣ በድህነት ቤት የተረከቧቸውን ልጆቻቸውን ህይወት እናስበው !

በእህቶቻችን ደልላ የበለጸጉት ክፉዎችን ዛሬ ወደ ፍርድ የሚያቀርባቸው ቀርቶ ዝንባቸውን ” እሽ ” ማለት የሚቻለው የለም ! ይባስ ብለው ዛሬ ዳግም ወደ አረብ ሃገራት የተዘጋው የኮንትራት ስራ ይጀመር ዘንድ እያጎበጎቡ ነው! ይባስ ብለው የኮንትራት ስራው የመጀመሩን ለእነሱ የሃሴት ለእኛ መርዶ የሚሆነውን ቀን መቅረብ ባለጊዜዎች ናቸውና በድፍረት እየነገሩን ነው! ይህም ያማል ፣ ያማል ፣ ያማል :(

ባደገች በተመነደገች ሃገራችን እየሆነ ያለውን ላሰበው ያማል …ያኔ ታዋቂው ድምጻዊ ዶር ጥላሁን ገሰሰ በቂ ህልምና የሚያገኝበት ሆስፒታል ጠፍቶ መንከራተቱን አስታውሰን ፣ የሃናን የህክምና ተቋማት ግፍ የተፈጸመባትን እህት መታደግ አለመቻላቸውን ስናስበው ልባችን በሃዘን ይሰበራል :( ይህም ያማል ፣ ያማል ፣ ያማል ይህም ያማል ! ዛሬ ህመማችን ጸንቷል ፣ የጸናው ህመም የሚታከመው ደግሚ ትክክለኛ ፍትህ ስናገኝ ብቻ ነውና ፍትህን ተጠምተናል ፣ ፍትህን እንሻለን !

ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 13 ቀን 2007 ዓም

በሚኒሶታ በመኪና አደጋ ሕይወታቸው ያለፈው የ61 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ አባት ፍትሃት ዛሬ እሁድ ይደረጋል

$
0
0

አቶ ለሙ መሹ የተባሉ የ 61 ዓመት ኢትዮጵያዊ አዛውንት በድንገተኛ የመኪና አደጋ በሚኒሶታ ሕይወታቸው ማለፉን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም:: የ እኚህ ኢትዮጵያዊ አባት የፍትሃት ስነስርዓት ዛሬ እሁድ ኖቬምበር 23 ቀን 2014 ዓ.ም እንደሚካሄድ ከቤተሰቦቻቸው አካባቢ ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ያመለክታል::
ኢትዮጵያዊው አባት ሕይወታቸው ያለፈው አስፓልት በሚሻገሩበት ወቅት ሲሆን የገጫቸው መኪናም ሳይረዳቸው መሄዱንም በሚዲያዎች ተዘግቧል::
FullSizeRender
ከቤተሰቦቻቸው የደረሰን መል ዕክት የሚከተለው ነው:-

አቶ መሹ ቡልቶ ለሙ በ 1953 ዓመተ ምህረት ከአባታቸዉ ከአቶ ቡልቶ ለሙ እና ከናታቸዉ ከወይዘሮ ሃታቱ ጅንዶ በሽዋ ክፍለ ሃግር በግንደ በረት ወረዳ ተወልደዉ ማክሰኞ November 18, 2014 በደረሰባቸዉ ድንገተኛ አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። አቶ መሹ ቡልቶ ከሶስት አመታት በፊት ለልጆቻቸዉ ለወደፊት የትምህርት እድል እንዲያገኙ በማሰብ ወደ አሜሪካ አገር የመጡ ሲሆን ዉድ ባለቤታቸዉን እና ልጆቻቸዉን ለማስመጣት በዝግጅት ላይ እንዳሉ በድንግተኛ አደጋ ህይወታቸዉ አለፈ፤። ቤተ ሰቦቻቸዉ እና ወዳጅ ዘመድ ሁሉ እንዲሁም በአጠቃልይ በሚኒሶታ የምንኖር ኢትዮጵያዉያን የተሰማንን መሪሪ ሃዘን እንገልጻለን፤ ለቤተሰቦቻቸዉ ም እግዚአብሔር መጽናናትን ይስጥልን።

የአቶ መሹ ቡልቶ ጸሎተ ፍትሃት በመጭዉ እሁድ November 30,2014 በደብረ ብርሃን ቅዱስ ኡራኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከጧቱ 10:00am ሰዓት ጀምሮ ይከናወናል። ለወንድማችን አቶ መሹ ቡልቶ ለሙ (ወልደሰንበት)
ከቅርብ ጓደኞቹ
የፍትሃተ ጸሎት የሚከናወንበት አድራሻ
አድራሻ፦ 1144 Earl Street St. Paul, MN 55106
ሰዓት 10:00am
ስልክ : 763 412 5279

አንድነት አሁንም ቀሪ ሒሣብ አለበት!

$
0
0

ከይድነቃቸው ከበደ

“አያገባኽም፣ማን ደረሰብህ፣የራስህን ስራ ሥራ” እና የመሳሰሉ ምክሮች ከትችት ማምለጫ የሞኙ-አሞኝ ቀፋፊ አካሄድ ነው፡፡ሁሉ ነገር በእጄ ነው የሚለው ገዥው የወያኔ መንግሳት ከመተቸት እና ከማጋለጥ ከፍ ሲልም ከስልጣኑ ለማውረድ ሞራል አለኝ የሚል ሰው ፣ማንኛውንም ፓርቲ እና ግለሰብን ለመተቸት እና ለማጋለጥ የሚያፈገፍግ እንደማይሆን እርግጥ ነው፡፡

ይድነቃቸው ከበደ

ይድነቃቸው ከበደ


እኔም ከዚህ የተለየ እምነት የለኝም፡፡ በማልስማማበት እና ቅር በተሰኘሁበት ጉዳይ አስተያየት የመስጠት ልምዴን እያዳበርኩ የምገኝ ፣ለመተቸት እና ለመማር እራሴን የዘጋጀው ነኝ፡፡ሌላው ቀርቶ እኔ በሃላፊነት ያለሁበት ፓርቲ የተሳሳተ ሃሳብ እና አቋም የያዘ ሲመስለኝ በግሌ ትችት አዘል አስተያየት በጋዜጣ፣በመፅሔት እና በተለያዩ ዌብሳይቶች ላይ በፁሑፍ ይገኛል፡፡ ከእነዚህም መካክለ “ወደፊት ቆሞ ወደ ኋላ መመልከት”፣ “ጥያቄው ሃይመኖታዊ ነፃነት መብት ወይስ ፖለቲካዊ ” እና “ድንጋይ ቢቆሉት አይሆንም ቆሎ ”የመሳሰሉት የገኝበታል፡፡

ይህ በእንዲ እንዳለ አንድነት ፓርቲ “በምርጫ እሳተፈላው” በማለት ያወጣው መግለጫ ከሰሞኑ የመነጋገሪ ዕርስ እንደነሆነ ለማናችንም ግልፅ ነው፡፡ ይሄን ተከትሎ “በምርጫ ለመሳተፍ ጋዜጣዊ መግለጫ ለምን ?” በማለት የግል ዕይታዬ ገልጫለው፡፡በዚህም ምንያት ትችት እና አስተማሪ የሆነ አስተያየት በፊስቡክ ገፄ እና ሣጥኔ በግል መልዕክት እንዲሁም ባመቻቸው መንገድ የሰጡኝ አስተያየት ደርሶኛል፡፡ ለዚህም አስተያየታችሁ ምስጋናዬ ከፍ ያለ ነውና በያላችሁበት ይድረሳችሁ፡፡

እኔም ሆንክ ሌሎቻችን በሰጠነው ትችት እና አስተያየት አንድነት ፓርቲ ጉዳዩን ለማጥረት በዛሬው ዕለት “አንድነት የፀረ ሽብር አዋጁ ተቀብሎትም አያውቅም፤ አይቀበለውም!” በማለት ያዋጣው መግለጨ የሚበረታታ እና የሚደነቅ ነው፡፡ በፀረ ሽብር አዋጁ ላይ አንደነት የሰጠው ማብራሪያ የሚደግፍ ቢሆንም በምርጫ ላይ ያለው አቋም ግን የፀና መሆኑ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች በማህበራዊ-ድረ ገፃቸው እንዲሁም በተለያየ መንገድ አረጋግጠዋል፡፡ይህን አቋማቸው እና የትግል ስልታቸውን አከብራለው ፡፡ የሚያዋጣቸውም ከሆነ ወደፊት በጋራ የምናየው ይሆናል፡፡

አሁን ላይ አስቀድሞ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ፣ ለዛውም አቋምን ለመግለፅ አስገዳጅ ሁኔታ ባልተፈጠረበት፣ “ምርጫ እሳተፋለው” ማለት ለቀጣይ የትግል ስልት ለፓርቲው(ለአንድነት) የስልጣን ባለቤትነት የሚያበቃው ከሆነ መንገዱን ጨርቅ ያድርግለት፡፡ለመረጃ ያኸል አንድነት አወጣ የተባለው መግለጫ ሾልኮ የወጣ እንጂ የታሰበበት እንዳልነበር እየወጡ ያሉ መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ ለዚህም ማረጋገጫ የሚሆነው “የአንድነት የምርጫ ጉዳይ ግብረ ሃይል” በጉዳዩ ዙሪያ የሚያወቀው ነገር እንደሌለ እና በዚህም ምክንያት በአንድነት ቤት ውጥረት እንደሰፈነ፣በተጨማሪ በአቶ ግርማ ወቅታዊ አቋም ከጥርጣሬ ባለፈ “ጫጫታ” እንዳለ የአንድነት ፓርቲ ወፍ ነግራኛለች፡፡ወፏ ደግሞ ለእኔ ታማኝ ናት፡፡

ሌላው እና ዋናው ጉዳይ አቶ ግርማ በተመለከተ ነው ፡፡ አቶ ግርማ የአንድነት ፓርቲ ም/ት ሊቀመንበር መሆናቸው የሚታወቅ ነው፡፡ይሁን እንጂ እነደሳቸው አገላለፅ የግሌ ሣይሆን የፓርቲየ አቋም ነው በማላት ስለሚናገሯቸው ነገሮች እና ስለሚፁፏቸው ጹሑፍ መጠነኛ ምልከታዬን ለመግለፅ እወዳለው፡፡አንድነትም ያላወራረደው ቀሪ ሒሣብ ያለበት እዚህ ላይ ነው፡፡ እዴት ለሚለው ይህን እንመልከት፡፡

1ኛ. በድረ-ገፃቸው በ “ፀረ ሽብር ህግ” ተከሰው ቅጣት ከተጣለባቸው ውስጥ ቅጣት የሚገባቸው ተከሳሾች የሉም የሚል ጭፍን ዕየታ የለኝም፡፡ እነዚህ ሰዎች በወንጀል ህጉ ሊቀጡ የሚችሉ እንደሆነ ግን መቶ በመቶ እርግጠኛ መሆን ይቻላል፡፡”ማለታቸው ከምን የመነጨ ነው ! በ “ፀረ ሽብር ህግ” ተከሰው ቅጣት የተጣለባቸው እና ቅጣታቸውን የሚጠብቁ 1ኛ.ናትናኤል መኮንን 2ኛ.አበበ ቀስቶ 3ኛ.አንዱአለም አራጌ 4ኛ.እስክንድር ነጋ 5ኛ.ርእዮት ዓለሙ 6ኛ.በቀለ ገርባ በተጨማሪ ሌሎች ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች፣ ጦማሪያን፣ የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊዎች፡፡ በአቶ ግርማ አገላለፅ እነዚህ ሽብርተኞች በወንጀል ህጉ ሊቀጡ የሚችሉ መሆናቸው መቶ በመቶ እርግጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
Girma  Seifu
2ኛ.ሌላው ደግሞ አቶ ግርማ በድምፅ ከተናገሩት “……ሁሉ ጊዜ ከመንግስት ጋር “እንትን” የምንለው በኢትዮጵያ ሰላም እና ፀጥታ፣ ችግር ይፈጥራሉ ብሎ የሚባል ነገር ካለ እኛም የበለጠ ያጋባንል….” ይቺ ናት ጨዋታ! የት ነበር ይሄን ዘፈን የሰማሁት ? አቶ ግርማ ስለሚናገሩት ነግር ምን ያህል እርግጠኛ ስለሞሆናቸው እጠራጠራለው፣ይሄን ንግግር የተናገሩት ከ“ፀረ ሽብር ህግ” ጋር በተያያዘ ነው፡፡መንግሰት ደግሞ እስካሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከገዥው መንግሰት የተለየ ሃሳብ ያለውን በሙሉ “የሕዝብን ሰለምና ፀጥታ፣ለማደፍረስ” በሚል የሽብር ክስ የሚመሰርተው እና የሚያስረው እንዲሁም የሚያሰቃየው ፡፡እንደ አቶ ግርማ አገላለፅ ከመንግስት እኩል ፓርቲያቸው እንደሚያስጨንቀው የገለፁት፡፡

ነገሩን ይበልጥ ግልፅ ለማድረግ “የአ.አ አሰተዳደር ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እርምጃ እወስዳለው” ማለቱ የሚታወቅ ነው፡፡ አስተዳደሩ ይሄን ያለበት ምክንያት ደግሞ ለማንም ግልፅ ነው፡፡ በአቶ ግርማ ቀመር መሠረት ከምንግሰት እኩል ጉዳዩ አግብቷቸው እሳቸው እና ፓርቲያቸው እርምጃ ሊወስድ ነው ማለት ነው ? እንዴን ግምት አቶ ግርማ ሊያደርጉት ይችላሉ፣ፓርቲያቸው ግን ይሄን የሚያደርግ አይመስለኝም ፣ከአይመስለኝም ወደ እርግጠኝነት የሚያሸጋግረኝ፤ አንድነት ፓርቲ በዚህ ላይ ያለውን አቋም ለክ እንደ ፀረ ሽብር አዋጁ በግልፅ ካሳውቅ ነው፡፡ለዚህም ነው “አንድነት አሁንም ቀሪ ሒሣብ አለበት” !ያልኩት፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !


የሬድዮ ስርጭት ኢንጂነሩ አረፉ

$
0
0

Breking Newsበራድዮ ስርጭት ኢንጂነር የሆኑት ኢንጂነር ከበደ ጎበና ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመለከተ:: በብስራተ ወንጌል ራድዮ ጣቢያ በሬድዮ ስርጭት (ትራንስሚተር) በዋና አዘጋጅነትናና በዋና ኢንጂነርነት እንዲሁም በማስታወቂያ ሚ/ር ጡረታ እስከወጡበት ድረስ በራድዮ ስርጭት ኢንጂነርነት ያገለገሉት ከበደ ጎበና ሕይወት ታሪክ ከቤተሰቦቻቸው ለዘ-ሐበሻ ደርሷል እንደሚከተለው አስተናግደነዋል::

Click Here

መተቸት መብት ነው- ግን መረጃ እየያዝን (መልስ ለአቶ ይድነቃቸው) –ግርማ ካሳ

$
0
0

አቶ ይድነቃቸው የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ናቸው። አንድነት ፓርቲ ላይ ያነጣጠረ ሁለት ጽሁፎችን በቅርቡ ለቀዋል። እንደ አንድነት ደጋፊ አንድነት ላይ ትችት መቅረቡን አልቃወምም። ሆኖም ትንሽ የመረጃ ክፍተት ሳይኖርባቸው እንደማይቀር በመገመት እንደሚከተለው ምላሽ ስጥቻለሁ፡

ወንድም ይድነቃቸው፡

“እኔም ሆንክ ሌሎቻችን በሰጠነው ትችት እና አስተያየት አንድነት ፓርቲ ጉዳዩን ለማጥረት በዛሬው ዕለት “አንድነት የፀረ ሽብር አዋጁ ተቀብሎትም አያውቅም፤ አይቀበለውም!” በማለት ያዋጣው መግለጨ የሚበረታታ እና የሚደነቅ ነው፡፡” ብለ በጻፉት ላይ አስተያየት እንድሰጥ ይፍቀዱልኝ።

unnamed (2)ይመስለኛል አንድነት በጸረ-ሽብርተኝነት ሕግ ላይ ያልጠራ ነገር እንደነበረዉና አሁን በመግለጫው እንዳጠራው የሚገልጽ እድምታ ያለው ሐሳብ መሰለኝ ያስቀመጡት። አስተያየቶትን በነጻነት ለመጻፍና ለመናገር መብትዎትን እየተለማመዱ መሆንዎትን አደንቃለው። ማንም የተቃዋሚ ድርጅት ሆነ የተቃዋሚ መሪዎች ሁልጊዜ ቻሌንጅ ሊደረጉ ይገባል። ቻሌንጂን የሚፈሩ አምባገነን ባህርሪ ያላቸው ብቻ ናቸው ።

ሌላው “ አቶ ግርማ ሰይፉ “……ሁሉ ጊዜ ከመንግስት ጋር “እንትን” የምንለው በኢትዮጵያ ሰላም እና ፀጥታ፣ ችግር ይፈጥራሉ ብሎ የሚባል ነገር ካለ እኛም የበለጠ ያጋባንል….” ያሉትን ጠቅሰዉ “ይቺ ናት ጨዋታ” ብለዉም ጽፈዋሃል።

ይመስለኛል የሕግ ባለሞያ ሳይሆኑ አይቀሩም። የናንተ የሰማያዎችን አቋምን አላውቅም። አንድነት ግን ጠንካራ ጸረ-ሽብርተኛ አቋም ያለው ድርጀት ነው። እንደ አልካይዳ፣ አልሻባብ የመሳሰሉ ድርጅቶችን ለመዋጋት የሚደረገዉን አለም አቀፍ ጥረት ይደጋፋል። በተለይም አል ሻባብ የአካባቢያችን ትልቅ ጠንቅና ካንሰር እንደሆነም ያምናል። እንደ አይሳስ፣ ቦኮ ሃራም ያሉትን ይቃወማል። ይህን አቋም መያዝከህወሃት/ኢሕአዴግ ጋር መመሳሰል አይደለም።

ስለዚህ አቶ ግርማ ሰይፉ እንዳሉት በአገራችን ሰላምን ለማናጋት የሚሞክሩ ኃይላት ካሉ የአገር ሰላምና ጸጥታ አንድነትን ያገባዋል። ወንድሜ እኔ እስከሚገባኝ የአንድነት አላማና ራእይ ኢትዮጵያን ማዳን ነው። የእንግሊዘኛ አባባልን ልጠቅምና “ Andinet ( UDJ) is not against anyone ; but is FOR Ethiopia”.

unnamed (1)ጸረ-ሽብርተኝነት እና ሽብርተኛ የሆነው የጸረ-ሽብርተኝነት ህጉ የተለያዩ ነገሮች ናቸው። አንድነትን የሚተቹት “ለምን ሽብርተኝነት ላይ ጠንካራ አቋም ያዘ  ? “ ብለው ከሆነ ይንገሩን ። ይሄን ይላሉ ብዬ አላስብም። አርስዎም እንደ አይሰስ ያሉ ሽብርተኞችን አጥብቀው የሚቃወሙና የሚከሱ መሆንዎታን  ስለማወቅ።
አንድነትን የሚተቹት “የጸረ-ሽብርተኝነት ሕጉን ይደግፋል” ብለው ከሆነ ደግሞ መረጃ ያቅርብልን። እኛም ትችትዎትን እንድነጋራ። ግን የሚያቀርቡት መረጃ አይኖርም። ለምን የአንድነት ፓርቲ በስራው አቋሙን ያስመሰከረ ነውና። የአንድነት ፓርቲ ሕዝብ አደራጅቶ በይፋ በአደባባይ የጸረ-ሽብርተኝነት ህግን ተቃዉሞ፣  ሲንቀሳቀስ ለማየት የሚከተሉትን ፎቶውፖች መመለክቱ ብቻ ይበቃል። መቃወም፣ መተቸት መብት ነው። ግን በተቻለ መጠን አገናዝበንና መረጃ ይዘን ብናደርገውው ደግሞ የበለጠ ጥሩ ይሆናል።

ከዚህ በታች ያሉት ፎቶዎች እንደሚያሳዩት፣ አሁን ለሕሊና እስረኞች ተቆርቋሪ ነን የሚሉቱ ጡሩምባ ከመንፋታቸው በፊት፣ አሁን የጸረ-ሽብርተኝነት ሕጉ የሚቃወሙ ፊታወራሪዎች ከመነሳታቸው በፊት፣ የአንድነት ፓርቲና አንድነቶች ናቸው ለሕሊና እስረኞች አጋርነት በማሳየት፣ እስረኞች እንዲታሰሩበት ምክንያት የሆነው የጸረ-ሽብርተኝነት ሕግ እንዲሰረዝ፣ ከሶሻል ሜዲያዉና ከመግለጫም ባለፈ፣ ህዝብ ጋር በመዉረድ፣ ህዝብን በማስተባበር ሲጮሑ የነበሩት። ከአንድ አመት በፊት በአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ዉጭ ባሉ ከተሞች በተደረጉ ሰልፎች የነበረዉን በጥቂቱ ይመልከቱ። “የጸረ-ሽብርተኝነት ሕግ ሕግ መንግስቱን የጣሰ ነው” ወዘተረፈ የሚሉ መፈክሮችን ያንብቡ። ሐቁ እንግዲህ ይሄ ነው።

ዉድ አቶ ይድነቃቸው፤

unnamedበርግጥ የጸረ-ሽብተኝነት ሕግ እንዲሰረዝ፣ ለዉጥ እንዲመጣ፣ የሕሊና እስረኞች እንዲፈቱ ፍላጎት ካልዎት እንደ አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ በሶሻል ሜዲያ ያለፈ ህዝብን የማደራጀት ሥራ እርስዎና ድርጅትዎ ለመስራት ሞክሩ። የአንድነት ፓርቲ በቅርቡ ባባህር ዳር፣ በአዳማ፣ በመቀሌ በመሳሰሉ ጽ/ቤቶችን በአዲስ መልክ አጠናክሮ በየከልሉ ህዝቡ ጋር ወርዶ እያደራጀ ነው። በአዲስ አበባ በ23ቱም ወረዳዎች በአሥሩም ክፍለ ከተማው መዋቅሩን ዘርግቶ ወደ ህዝብ እየወረደ ነው። እናንተ እዚያ ላይ በርቱ።
አንድነት ፓርቲ ምርጫዉን ለመሳተፍ በወሰነው ዉሳኔ ላይ  ባቀረቡት ትችት ላይ ደግሞ፣ የርስዎ ድርጅት የምርጫ ምልክት ከጥቂት ቀናት በኋላ እንደሚወስድና እንደማይወስድ ካየን በኋላ መልስ የምንሰጥብት ጉዳይ ይሆናል። ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ምልክት ከወሰደ በኦፊሴል ምርጫዉን ለመወድዳደር ወስኗል  ማለት ነው። የምርጫ ምልክት ለምርጫ ለመወዳደር እንጂ ግድግዳ ላይ ሊሰቅል የሚወሰድ ባለመሆኑ።

 

 

 


ስጋት ላይ የወደቀዉ የአፍሪቃ የኤኮኖሚ አንቀሳቃሽ ሞተር

$
0
0

አዜብ ታደሰ

ተክሌ የኋላ

የጀርመኑ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር የጀርመን የቅርብ አጋር የሆነችዉን አፍሪቃዊት ሃገር ደቡብ አፍሪቃን ጎብኝተዋል። በደቡብ አፍሪቃ የጀርመኑ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የኤኮኖሚ አለመመረጋትና ደካማ ጎኖች አሉት በሚል ስጋት ላይ በመዉደቁ፤ የጀርመን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር የፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር ላይ ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎአል።

የጀርመኑ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር

የጀርመኑ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር

ስጋት ላይ የወደቀዉ የአፍሪቃ የኤኮኖሚ አንቀሳቃሽ ሞተር በሚል የዶቼ ቬለዉ ክላዉስ ሽቴከር ከፕሪቶርያ በላከዉ ዘገባ የጀርመኑ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር በደቡብ አፍሪቃዉ ጉብኝታቸዉ አንድ ምልክትን ማሳረፍ እንደሚፈልጉ በዘገባዉ አትቶአል።

የጀርመኑ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር ወደ ደቡብ አፍሪቃ ጎራ እንደሚሉ ሳይሰማ ነዉ፤ ጉብኝታቸዉን በድንገት የጀመሩት። የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከፕሪቶርያ ብዙም ከማይርቀዉ « ዋተር ክሎፍ» በተሰኘዉ የጦር አዉሮፕላን ማረፍያ ሲደርሱ በደቡብ አፍሪቃ እንደተለመደዉ፤ አንድ ታዋቂ ፖለቲከኛ በፖሊስ አቀባበልና አጃቢ እንደሚኖረዉ ሁሉ፤ የጀርመኑ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሽታይና ማየር አጃቢ ፖሊሶች አልነበሩዋቸዉም፤ አልመጣላቸዉምም። የዚህ ምክንያቱ ምን ይሆን? የአሰራር ጉድለት ወይስ ደቡብ አፍሪቃ ከቻይናና ከ«BRICS» ማለት በኤኮኖሚ በማደግ ላይ የሚገኙት የአምስቱ ሀገራት ጥምረት ሃገራት መንግስታት ጋር ያለዉ ግንኙነት የተሻለ ሆኖ በመገኘቱ? እንድያም ሆኖ የጀርመኑ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር ይህን ሁኔታ ትልቅ ትኩረት አልሰጡትም። ምንም እንኳ ሽታይን ማየር እየሩሳሌም እና ሞስኮ ላይ የሚደርጉት ድርድር አንዱ መረሃ-ግብራቸዉ እንዲሁም ስለኢራን የአቶም ጉዳይ ለመደራደር ወደ ቬና መሄድ ቢኖርባቸዉም የአፍሪቃዉን ጉዳይ በማስቀደም ወደ አፍሪቃ ተጉዘዋል።

Deutschland Präsident des Markenverbands Franz-Peter Falkeየካልሲ እና ስቶኪንግ ፋብሪካ ፔተር ፋልከ ዋና ተጠሪ

በግዜ እጥረት ምክንያት ወደ ኬንያ፤ ኮንጎ እና ሩዋንዳ አቅደዉንት የነበረዉን ጉዞ ቢሰርዙም ወደ ደቡብ አፍሪቃ መጓዛቸዉን እንደ ተጠበቀ ሆኖ ወደ ደቡብ አፍሪቃ አቅንተዋል። ጀርመን አጋሮችዋ ከሆኑት የአፍሪቃ ሃገራት መካከል ለደቡብ አፍሪቃ ቀዳሚዉን ቦታ ሰታለች። ሽታይን ማየር በዚህ ጉዞአቸዉ በድጋሚ የገለፁት ባለፈዉ ግዜ የነበረዉ አሰራር መቀየር እንዳለበት ነዉ። ማለትም አስቸኳዩ ጉዳይ የአዉሮጳና የጀርመን ከአፍሪቃ ጋር ያለዉ ወዳጅነት ቅድምያ ሊሰጠዉ ይገባል ነዉ ያሉት። ስለዚህም ምንም እንኳ የጊዜ እጥረት ቢኖርባቸዉም ወደ ደቡብ አፍሪቃ መምጣታቸዉ በድጋሚ ገልፀዋል። « በእዉነቱ ከሆነ አሁን አሁን ወደ አፍሪቃ መጓዝ ያስፈልጋል አያስፈልግም የሚለዉ ጥያቄ መታሰቡ አይቀርም ። ግን እንደኔ እንደኔ ቀደም ሲልም ሁኔታዉ እንዲሁ ነበር። ሁሌም ቢሆን አዉሮጳና ጀርመን ከአፍሪቃ ጋር ካላቸዉ ግንኙነት ይልቅ ለሌላዉ ነበር ክብደት ይሰጠዉ ነበር። እንደኔ እምነት ይህን አያያዝና ሁኔታ መቀየር ይኖርብናል። ለዚህም ነዉ በዚህ ግዜ ወደ አፍሪቃ መጓዝ ያስፈለገዉ። »

ሽታይን ማየር በደቡብ አፍሪቃ በሚያደርጉት ጉብኝት በሁለቱ ሃገራት መካካል ያለዉን ግንኙነት በአዲስ መልክ ለማጠናከር አቅደዋል። «ባለፉት ዘመናት አዉሮጳም ሆነች ጀርመን ከአፍሪቃ ጋር ያላቸዉ ግንኙነት ሌላ መልክና ባሕሪ ነበረዉ ያሉት ሽታይን ማየር እንዲሕ አይነቱ አስተሳሰብ ባሁኑ ወቅት መለወጥና መወገድ አለበት ብለዋል። በዚሕ ወቅት በአፍሪቃ የማደርገዉ ጉብኝትም በአዲሱ መንፈስ ላይ የተመሠረተ ነዉ» ሲሉ ሽታይን ማየር አክለዋል።

የጀርመኑ ዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሽታይን ማየር በጆሃንስበርግ በሚገኙ የጀርመን ባለወረቶች ፊት ቀርበዉ ባደረጉት ንግግር የጀርመን ደቡብ አፍሪቃ ባህላዊ ትስስርን አወድሰዋል። የጀርመኑ የሲመንስ ድርጅት በኬፕታዉን ከተማ በ 160 ዓመታት ጥሩ ተስፋን ማሳየቱም ተመልክቶአል። በደቡብ አፍሪቃ 600 የጀርመን ባለወረቶች የተለያዩ ድርጅቶችን ያቋቋሙ ሲሆን ድርጅቶቹ ለ 90 ሺ ሰራተኛ የስራ እድልን ፈጥረዋል። ጀርመን ለደቡብ አፍሪቃ ከቻይና ቀጥላ ዋንኛ የንግድ አጋር ሀገር መሆንዋም ይታወቃል። ደቡብ አፍሪቃ ለጀርመን ባለወረቶች አማላይ ናት ሲሉም ሽታይንማየር በንግግራቸዉ ሀገሪቱን አሞካሽተዋል። እንዲያም ሆኖ በስምምነት ረገድ ደቡብ አፍሪቃ ላይ እንከን መታየቱ አልቀረም። የጀርመን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሽታይን ማየር ጉብኝት ላይ የተጠበቁት የጉታንግ አዉራጃ ተጠሪ ጊዜ በማጣታቸዉ ምክንያት ተወካይን ነበር የላኩት። ይህ ታድያ አጋር ሃገር ጀርመንን ከማክበር ረገድ እንዴት ይታይ ይሆን?

በደቡብ አፍሪቃ የጀርመን ባለወረቶች ማኅበር በሃገሪቱ በሚታየዉ የፖለቲካ አለመረጋጋት ምክንያት መዋለ ንዋይ ለማፍሰስ ችግር ፈጥሯል ሲሉ ቅሪቸዉን ያሰማሉ። ጃኮብ ዙማ የሚመሩት የደቡብ አፍሪቃ መንግሥት የሃገሪቱን የኤኮኖሚ ፖሊሲ በተሳሳተ አቅጣጫ እየመራ ነዉ» ሲል በደቡባዊዉ አፍሪቃ የጀርመን የኤኮኖሚን አንቀሳቃሽ ተቋም በጽህሮቱ «ሳፋሪ» ወቀሳዉን ያሰማል። ሳፍሪ በአረቀቀዉ ጽሑፍ ጎታች ናቸዉ ያላቸዉን ሰባት እክሎች ጠቅሶአል። ከነዚህ መካከል ደግሞ አዲስ የፀደቀዉ የጥገኝነት ህግ ይገኝበታል። ሌላዉ በሃገሪቱ የባለወረቶች ስራን በተገቢ መመርያዎች አለመጠበቁ ነዉ። የጀርመን መንግስት በአፍሪቃ በሚገኙ 39 ሃገራት ለባለወረቶች ከለላ ለመስጠት የሁለትዮሽ ስምምነትን መድረሱ ይታወቃል። ከአንድ ዓመት ግን በፊት ደቡብ አፍሪቃ ይህን ዉል አፍርሳለች። ሃገሪቱ በምትኩ ያፀደቀችዉ የብሄራዊ ህግ ደግሞ ከዉጭ ለሚመጡ ባለወረቶች ከፍተኛ ፈተናና አደጋን መደቀኑ ነዉ የተነገረዉ።

የካልሲ እና ስቶኪንግ ፋብሪካ ፔተር ፋልከ ተጠሪ እንደሚሉት በዚህ ረገድ የአሰራር ሂደት ስህተት እንዳለ አመላካች ነዉ። «ይህ በእዉነቱ አስደንጋጭ ምልክት ነዉ። በርካታ ባለወረቶች በደቡብ አፍሪቃም ሆነ በሌሎች የአፍሪቃ ሃገራት ገንዘብን አፍሰዋል። በደቡብ አፍሪቃ በማዕከላዊነት መንቀሳቀስ የሚፈልጉት ግን በአንፃሩ እጅግ ስጋት ላይ ወድቀዋል፤ እናም ስራ ላይ ያዋሉትን ወረታቸዉን ይዘዉ መመልስን ነዉ የሚሹት» በኬፕታዉን የሚገኘዉ ፋክቶ የተሰኘዉ ካልሲና ስቶኪንግ አምራቹ ድርጅት ስራዉን ከጀመረ 45 ዓመታትን አስቆጥሮአል። በሀገሪቱ አሁን እንደሚታየዉ የአሰራር አካሄድ ከሆነ አምራች ድርጅቱ ብዙም ዘለቂታዊ ስራን ባልያዘ ነበር።

የፖለቲካ አለመረጋጋት ለጭንቀት መፈጠር ምክንያት ነዉ። ከጥቂት ቀናቶች በፊት አንድ የምክር ቤት አባል ፕሪዚደንት ዙማን «ሌባ» በማለቱና የምክር ቤት ፕሪዚዳንትዋን በትክክል ሳይጠራ በመቅረቱ ብሔራዊ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ታጣቂ ፖሊሶች ተገኝተዉ ሊያስወጡት መጥተዉ እንደነበር ተገልጾአል። በደቡብ አፍሪቃዉ 20 ኛ ዓመት ዲሞክራሲ ይህን ማየት እጅግ አስደንጋጭ ነዉ ሲሉ በደቡብ አፍሪቃ ምክር ቤት ህገ መንግስታዊ እድገት ጉዳይ ተመልካች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ላዉሶን ናይዶዉ ገልፀዋል። የማንኛውም ባለወረት ተቀዳሚ ትኩረት፣ አንድ ሀገር የፖለቲካዊ ሁኔታው የተረጋጋ መሆኑ ላይ ነዉ። እኛ መስቀለኛ መንገድ ላይ ቆመን ነዉ ያለነዉ ። የታጠቁ ፖሊሶች ወደተከበረው የፓርላማ አዳራሽ ገብተዉ አንድ የፓርላማ አባልን ሲያስወጡ ማየት በጣም ከፍተኛ ስጋት ላይ ይጥላል። እንዲህ ዓይነቱን ነገር በኛ ዲሞክራሲያዊ ማኅበረሰብ እናያለን ብለን መቼም አስበነዉ አናዉቅም»

Südafrika Parlament in Cape Town Screenshot Chaosበደቡብ አፍሪቃ ብሔራዊ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ታጣቂ ፖሊሶች የታዩበት ምስል

የጀርመን ባለወረቶች እና የደቡብ አፍሪቃ የሲቢል ማኅበረሰብ በጋራ የደቡብ አፍሪቃ የኤኮኖሚ ይዞታ ያሳስባቸዋል። ይሄም የፖለቲካ ዉይይት ላደረጉት የጀርመን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር ግልፅ መልክት ሆኖ ቀርቦላቸዋል። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ላዉሶን ናይዶ በበኩላቸዉ በደቡብ አፍሪቃ ብሩህ መፃይ እድል መኖሩን ነዉ የተናገሩት።እንደ ላዉሶን ናይዶ የኔልሰን ማንዴላና የዴዝሞን ቱቱን ራዕይ እዉን ለማድረግ የደቡብ አፍሪቃ ዴሞክራሲ ከ 20 ዓመት ወዲህም ቢሆን እንደብረት ጠንክሮ ነዉ የሚገኘዉ። ስለሆነም ጠንካራዉ ኤኮኖሚ አንዳንዴ በሚዋዥቀዉ የፖለቲካ አካሄድ መጽናናቱ አይቀሪ ነዉ።

ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር በደቡብ አፍሪቃ በሚያደርጉት ጉብኝት ከፖለቲካ አቻዎቻቸዉ ጋር በሚያደርጉት ዉይይት ስጋት ባልዋቸዉ ነጥቦች ላይ እንደሚነጋገሩ ገልፀዋል። በደቡብ አፍሪቃ የሚገኙት የፋልከ ቡድን የካልሲና ስቶኪንግ አምራች ድርጅት ፋራንዝ ፒተር ፋልክ ተጠሪ በበኩላቸዉ ሚኒስትሩ የሰከነ አቋምና ተግባር ዉጤታማ እንደሚያደርግ መተማመናቸዉን ገልፀዋል። የጀርመኑ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር በጉብኝታቸዉ ደቡብ አፍሪቃ፤ አፍሪቃ ዉስጥ ሠላም ለማስፈን የምታደርገዉ ጥረት በጣም ጠቃሚ እና አበረታች መሆኑን አስታዉቀዋል። እንደ ሽታይንማየር ደቡብ አፍሪቃ ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ እስከ ሱዳን ያሉ ግጭቶችን ለማስወገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦን እያደረገች ነዉ። ሽታይን ማየር በደቡብ አፍሪቃ በሚያደርጉት ጉብኝት በሁለቱ ሃገራት መካካል ያለዉን ግንኙነት በአዲስ መልክ ለማጠናከር እቅድ መያዛቸዉም ተገልፆአል።

 

በሰሜን ጎንደር የሕወሓት አማሳኞች ሰርገው የበመግባት ወጣቱን እያጋደሉ መሆኑ ተሰማ

$
0
0

-ከከተማው ለስራ የሄዱ ወጣቶች ንብረታቸውን እና ገንዘባቸውን ሳይሰበስቡ አከባቢውን ለቀዋል

ከሚኒልክ ሳልሳዊ

በኢትዮ ሱዳን ድንበር ላይ ለስራ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን መንደር እየለዩ በመቧደን በከፍተኛ ጭፍጭፍ ውስጥ እንደሚገኙ ከአከባቢው የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል::
news
ከሱዳን ጋር በተያያዘው እና የታች አርማጮ መሬት ከሆነው ሰቲቱ ሁመራ ማይካድራ ሉግዲ አብዲራፍ አብድራሃጀር መተማ ሸዲ የተወሰነውን ጠገዴ ያሉት የጎንደር መሬቶች ላይ በኢንቨስትመንት ስራ ላይ የተማሩ የሕወሓት አባላት የሆኑት የጊዜው ባለሃብቶች በቀተሯቸው እና ከአማራው ክልል ጎንደር ጎጃም እና ወሎ የመጡ ወጣት ገበሬዎችን እርሲ በራስ በመንደር እና በጎጥ በመከፋፈል እንዲተራረዱ እንዲጨራረሱ የሰሩበትን ገንዘብ ሳይሰበስቡ አከባቢውን በፍርሃት ለቀው እንዲሄዱ እያደረጉ መሆኑን መረጃዎቹ የሰሞኑን ከፍተኛ ግጭት አስመልክተው ጠቁመዋል::

በሉግዲ አከባቢ በዚህ ሰሞን ብቻ በጎንደር እና በጎጃም በወሎ እና በሸዋ በሚል የተቧደኑ ሰዎች በሕወሓት ኢንቨስተሮች ነገር አስፋፊነት ከፍተኛ ግጭት በመከሰቱ በርካታ ወጣቶች የተገደሉ ሲሆን ቀሪዎቹ ንብረታቸውን እና ገንዘባቸውን ሳይሰበስቡ ድንገት ግጭቱን ሸሽተው ወደ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የሄዱ መሆናቸው ታውቋል::

የሕወሓት አማሳኞች እና ሰላዮች በወጣቶቹ መካከል ሰርገው በመግባት እሪስ በ እርስ ጎጥና መንደር እንዲለይ አድርገው በማቧደን እርስ በ እርስ ሕዝቡ እንዲተራረድ አድርገዋል ሲሉ ምንጮቹ በላኩት መረጃ ተናግረዋል::በዚህ ሳምንት ብቻ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ በርካታ ሬሳዎች ወደ ሉግዲ ከተማ የተጓጓዙ ሲሆን ይህ የሕወሓት ሰላዮች/አማሳኞች የሚቀሰቅሱት የሰርጎ ገብነት ዝሴራ እስከ ማይካድራ ድረስ ተስፋፍቶ ከፍተኛ የደም መፋሰስ እና የዘር መጠፋፋት እየተደረገ መሆኑን አክለው ገልጸዋል::

ታዋቂው አርቲስት ባልተጠና የፊልም ቀረጻ ሜካፕ በገባለት የዓይን ኮንታክት ሌንስ የተነሳ የዓይን ብርሃኑን ለአንድ ቀን አጥቶ ዋለ

$
0
0

ከዘላለም ገብሬ

ለፊልም ስራ ወጥቶ በለበሰው ቀረጻው የኮንታክት ሌንስ ምክንያት አይኖቹ ለአንድ ቀናት ላለማየት ችሎ ነበር ። ይህም ሊሆን የቻለው የአይን ብሌኖቹ ውስጥ ተሰክተው የነበሩት ኮንታክት ሌንስ ለፊልሙ ስራ ሲባል እንዲያጠል የታዘዘ ሲሆን የአይኖቹን ብሌኖች ላይ ጫጭረውትተንደነበርረና ለረጅም ሰአታት አይኖቹ ሲያለቅሱ እንደነበር እና ጉዳቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እየጨመረ የመጣው የአይኑ ማልቀስ ሥሜት እስከ ሆስፒታል ድረስ እንዲሄድደና በባለሙያዎች እንዲታይ ተደርጎ መድሃኒት እንዲጠቀም አዘውት ነበር “ነገ እኮ ቴአትር አለኝ” እያለ ለቲያትር ስራው የሚጨነው አበራ ጆሮ በዶክተሮቹ ጫና አንተ አይንህ እየጠፋ ስለ ነገ ቴአትር ታስባለህ ሲሉት ምላሽ ሰጥተውታል ።
shimelis abera joro
ይህ በእንደዚህ እንዳለ ችግሩ እንዲቀል በታዘዘው መዳኒት ታግዞ እስከሚቀጥለው ማለዳ እንዲቆይ ታዟል:: በዚህ የከፋ ሁኔታ የሚደርስበት ከሆነ ግን ወደ ከፍተኛ ህክምና ለኦፕራሲዮን ሊላክከንደሚችልላሳውቀውት ተለይተዋል ።ሆኖም ግን ከአንድ ቀን በሁዋላ አይኑ ዳግም ወደ እይታ ሊመለስ እንደቻለ ኢትዮጲካን ሊንክ ጠቁⶁል ። ሆኖም ግን ከጥንቃቄ ጉድለትና የባለሙያዎች ድጋፍ ባለመኖሩ ለተደረገለት የሜካፕ ስራ አርቲስት ሽመልስ አበራ የቴአትርራ አጋጆቹን ለመክሰስ አለመክሰስ የተደረገ ምን አይነት መረጃ እንዳልተገለጸ ሲሆን ፣በሃገራችን በሚደረጉት የፊልምና የቴአትር ስራዎች ላይ የሜክአፕ አርቲስት ሆነው የሚያገለግሉት በሙሉ በሙያቸው ዘርፍ ሳይሆን ያለሙያቸው በመሆኑ ለብዙ ጉዳቶች ይዳጋል ።ይህንን ደግሞ ከግንዛቤ በማድረግ ለአይንም ሆነ ለሌላ የአካል ስራ መዋል ያለበት በሙያው ላይ የተካነ መሆን ይገባዋል።

ለእያንዳንዱ የአካል ስራ እንቅስቃሴ ሙያዊ እገዛን የሚጠይቅ ሲሆን ለአንድ ፊልም ደራሲ አዘጋጅ ፣ዳይሬክተር ወይንም ሌላም ሌላም አንድን ሰው ብቻ ማእረግ በመስጠት በሚሰራበት የኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ ይህ ኁኔታ መቀጣጫ ሊሆናቸው የሚገባ ሲሆን ፣ሽመልስ አበራ ጉዳዩን ከምን ሊያደርሰው እንደሚችል አልታወቀም ።

ቴዲ አፍሮ ለባለቤቱ አምለሰት ሙጬ የገጠመው ግጥም –እንኳን ማርያም አሜን

$
0
0

teddy afro
ከፍቅር ጸንሳ ልጅን ያህል ጸጋ
ወልዳ ተኝታለች ባልተቤቴ ካልጋ
ግቡና ጠይቋት አጎበር ገልጣችሁ
ሁለት ሆና ሚስቴን ታገኟታላችሁ፡፡
እኔ ሳልሳዊ ነኝ የቤቱ አባወራ
እጹብ እጹብ በሉ ይህን ድንቅ ስራ
በእናት መሬት ላይ በአባት ገበሬ ህጻን እየዘራ
ያንድ አምላክ ሚስጥሩ ሦስት ሆኖ ሲሰራ
ምሉዕ ከመ አምላክ የሚካኤል ስሙ
እንደ እግዚያብሄር ያለ ማንም ያለ ሲሆን የቃሉ ትርጉሙ
ራስን እንደ አዲስ ወልዶ ለመድገሙ
የማርያም ነው እና ሴትነት ቀለሙ፡፡
እንግዲህም አንቺ
አስመላሽ ነሽ እና ሲገሰግስ እድሜ በልጅ እያደስሽን
መልክ የምታሳዪ እንደ አዲስ ወልደሽ
እንኳን ማርያም አሜን፤
እንኳን ማርያም አሜን
ምስጋና ይድረሰው አንድ ላደረገው ስምሽና ስሜን፡፡
የውለታሽን ዳር በቃላት ለመድረስ ስላቃተው አቅሜ
ይሁንሽ ስጦታ የሚቀጥለው ዘፈን ከገለጸው ልቤን፡፡
አሜን!

ወሲብ እና ሁለንተናዊ ጤንነት

$
0
0

ሁላችንም ወሲብ አስደሳች እንደሆነ እናውቃለን፤ ይሁን እንጂ ለጤና ጠቃሚ ነው ወይ የሚል ጥያቄ አንስተን እናውቅ ይሆናል፡፡ መልሱ እጅግ በጣም የሚል ነው፡፡ ነዋሪነታቸውን ኒውዮርክ ከተማ ያደረጉ እና “She Comes First.” በሚል መጽሐፍቸው የሚታወቁት የወሲብና ወሲብ ነክ ጉዳዮች አማካሪ አየር ኬርነር #የወሲብ ህይወታችን ጤና የአጠቃላይ ጤና ነፀብራቅ ነው፡፡$ይላሉ፡፡

sex11በወሲብ ዙሪያ ጥልቅ ጥናትና ምርምር ያደረጉ ባለሙያዎች ወሲብ ለራሳችን የሚኖረንን አመለካከት (self-esteem) ከማሻሻል ጀምሮ ለውስን በሽታዎች የሚኖረንን ተጋላጭነት እስከ መቀነስ ድረስ ብዙ ጥቅም እንደሚሰጥ ያስረዳሉ፡፡ በአንፃሩ፣ እምብዛም ወሲብ የማይፈፅሙ ከሆነ ችግር ሊኖር ይችላል፡፡
እነዚህን ችግሮች ለይቶ መፍታት አስፈላጊ ነው ይላሉ ኬርነር፡፡ ምክንያቱም የወሲብ ህይወታችን በብዙ መልኩ ከልዩ ልዩ የሕይወት ክፍሎቻችን ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አለው፡፡ ለአብነት ያህል፣ የወሲብ ፍላጎትዎና አፋፃፀምዎ አናሳ ከሆነ ምንአልባት የድብርት ተጋላጭ ሊሆኑ ይችላሉ፣ ክብደትዎ ከልክ በላይ ሊሆን ይችላል፣ የተመጣጠነ ምግብ አይበሉ ይሆናል፣ ውጥረት ውስጥ ይገኙ ይሆና ወ.ዘ.ተ፡፡

ወሲብ ተከታዮቹን በመድሀኒት መልክ ሊገኙ የማይችሉ ጤና ነክ ጥቅሞች ይሰጣል፡-

የልብ ጤንነትዎን ሊያሻሽል ይችላል

ጥናቶች እንደሚጠቁሙት የብልት መጠንከር ከልብ መጠንከር ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው፡፡ በ2008 ዓ.ም የአሜሪካን የልብ ህክምና ጆርናል ላይ ይፋ የተደረገ ጥናት እንደሚያብራራው የብልት መቆም እና መጠንከር ችግር (erectile dysfunction (ED)) ከልብ ጥንካሬ ማጣት ጋር ግንኙነት አለው፡፡

ተመራማሪዎች 2300 ወንዶች ላይ ባደረጉት ምርምር መሠረት የብልት መቆም እና መጠንከር ችግር ያለባቸው ወንዶች ለልብ ህመም ያላቸው ተጋላጭነት ችግሩ ከሌለባው ይልቅ በ 58% ከፍ ነው፡፡

ለፕሮስቴትካንሰርየሚኖራአችሁተጋላጭነትሊቀንስይችላል

በ2004 ዓ.ም የአሜሪካ ህክምና ባለሙያዎች ማህበር ጆርናል ላይ 24000 ወንዶችን አሳትፎ ይፋ የተደረገ ጥናት እንዲሚጠቁመው በአንድ ወር ውስጥ 21 ጊዜ ወሲብ የሚያደርጉ ሰዎች በወር ውስጥ ከ4 – 7 ጊዜ ያህል ወሲብ ከሚያደርጉ ሰዎች ይልቅ ኋላ ላይ ለፕሮስቴት ካንሰር የሚኖራቸው ተጋላጭነት በእጅጉ ይቀንሳል፡፡

ለሥራይጠቅማል

ሔለን ፌሸር የሚባሉ ኦንትሮለፖሎጂት ወሲብ የፈጠራ አቅምን፣ ችግር የመፍታት ችሎታን እና የመግባባት ክህሎትን እንደሚያሻሽል ይገልፃሉ፡፡ ይህንን ሁሉ ነገር ሊያሻሽል የሚችልበት አብይ ምክንያት ወሲብ ስንፈፅም አንጎላችን ዶፓሚን እና ኦክሲቶሲን አካ የሚሰኙ የደስታ ስሜትን የሚያጎናፅፉ ኬሜካሎችን በብዛት አምሮቶ ስለሚያሰራጭ ነው፡፡

የወጣትነት መልክዎና ቁመናዎ ተጠብቆ እንዲቆይ ይረዳል

ስኮትላንድ ውስጥ 3500 አሜሪካውያንን እና አውሮፓዊያንን ያሳተፈ አንድ ጥናት ተካሂዶ ነበር፡፡ ጥናቱ ለአስር አመት ያህል ቢያንስ ቢያንስ ከ7 – 12 አመት ከእድሜቸው ይልቅ ወጣት የሚመስሉ ሰዎችን አፈላልጎ ማግኘትና የጋራ ጠባያቸውን ማጥናት ነበር፡፡ ታዲያ እነዚህ ሰዎች ታስሰው ከተገኙ በኋላ ጥናቱ የእነዚህን ሰዎች የጋራ መለያ ጠባይ ምን እንደሆነ ለመረዳት እና ለመተንተን ሙከራ አድርጓል፡፡ በግንባር ቀደምነት እነዚህን ወንዶች የሚያመሳስላቸው ነገር መደበኛ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ መቻላቸው ነው፡፡

ሁለተኛው የጋራ መለያ ጠባያቸው በመደበኛነት ወሲብ መፈፀም መቻል ነበር፡፡ ከሞላ ጎደል ሁሉም ከ 2 – 3 ጊዜ በሳምንት ከፍቅር ወይም ትዳር አጋራቸው ጋር ወሲብ ይፈፅማሉ፡፡

ውጥረትን ያረግባል

ሴቶች የእርካታ ጣሪያ ላይ ከመድረሳቸው ጥቂት ቀደም ብሎ በከፊል ንቁ በከፊል ንቁ ያልሆነ ሁኔታ ውስጥ ይገባሉ፡፡ በዚህ ወቅት ውጥረትን የመቀነስ እና የማርገብ ሚና የሚጫወተው የአንጎላቸው ክፍል ስራ ይጀምራል፡፡

አንጎልን ያነቃቃል

ዘወትር ወሲብ የመፈፀሚያ ተለምዷዊው መንገድ አስፈላጊ እንደሆነ ሁሉ አእምሮአችንን በወሲብ ሀሳብ ማነቃቃትም እንዲሁ አስፈላጊ ነው፡፡ ኬርነር የወሲብ ፍላጎት መነቃቃት የአካልና አእምሮ በጋራ መነቃቃት ነው ይላሉ፡፡ እኚህ ባለሙያ ብዙ ጊዜ አእምሮአችንን ማነቃቃት የሚችለው ሀሳብ ወሲብ ውስጥ ድርሻ ሊኖረው እንደሚገባ እንዘነጋለን ይላሉ፡፡

ኬርነር፣ ከዚህ በተጨማሪ ሁሉም የስሜት ህዋሳት ወሲብ ሲፈፀም ቦታ እንዲኖራቸው ማድረግ አስፈላጊ ነው ይላሉ፤ እይታ፣ ድምፅ፣ ንክኪ፣ ጣዕም፣ እና ጠረን፡፡

ስለዚህ፣ ቢያንስ ቢያንስ በሳምንት አንድ ቀን ወሲብ መፈፀም ብቻ ሳይሆን በተቻለ መጠን ሁሉንም የስሜት ህዋሳት እና ሁኔታወች ያካተተ አይነት ወሲብ መፈፀምን ያበረታታሉ፤ ምቾት፣ አዳዲስ ነገሮችን መሞከር እና ሁሉንም የስሜት ህዋሳት ተሳታፊ ማድረግ፡፡

ወሲብን የሚደግፉ እና የሚያበረታቱ ጥናቶች ቁጥር ስፍር የላቸውም፡፡ ስለዚህ የወሲብ አምሮታችሁ እና አድራጎታችሁ አናሳ ከሆነ ከዚህ ልምምድ ልትወጡ የምትችሉበትን ነገር ለማድረግ ሞክሩ፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የወሲብ ፍላጎታችሁ ማሽቆልቆል ከጀመረ ይህ ለምን ሊሆን እንደቻለ ለመረዳት ሞክሩ፤ የሳይኮሎጂ እና የህክምና ባለሙያ እንደየችግሩ ሁኔታ እገዛ ሊያደርጉላችሁ ይችላሉ፡፡ አለበለዚያ የተመጣጠነ ምግብ በመመገብ፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ፣ ለአካላችሁ እና አለባበሳችሁ ቦታ በመስጠት ቀላል የማይባል ለውጥ ማምጣት ትችላላችሁ፡፡ ኬርነር፣ ሰዎች ጤናማ ወሲብ ከፍቅር አልያም ትዳር አጋራቸው ጋር ማድረግ ሲችሉ ሕይወታቸው ይበልጥ ይደምቃል ይላሉ፡፡ ክብደታቸውን ለማስተካከልና ለመቆጣጠር ይበልጥ ተነሳሽነት ውስጣቸው ይፈጠራል፣ ራሳቸውን መንከባከብ ያዘወትራሉ፣ እንደተፈቀሩ ይሰማቸዋል፣ እርካታቸው ይጨምራል፣ ስራ ቦታ መነጫነጭም ሆነ መጋጨት ይቀንሳሉ፡፡ በጥቅሉ ወሲብ ለሁለንተናዊ ጤና መሻሻል በብዙ መልኩ አስተዋፅዖ ያበረክታል፡፡

ምንጭ፡ upwave.com

 

ለስብሰባ ሲቀሰቅሱ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ተጨማሪ 7 ቀናት ተቀጠረባቸው

$
0
0
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ጠርቶት ለነበረው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ አርብ ህዳር 5/2007 ዓ.ም በቅስቀሳ ላይ እንደነበሩ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ 7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡የአዲስ አበባ ከተማ ም/ሰብሳቢና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ማቲያስ መኩሪያ እና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ሳምሶን ግዛቸው በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ ሲሆን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ወጣቶቹ ‹‹ሽብር በማነሳሳት›› የሚል ‹ክስ› የተመሰረተባቸው ሲሆን ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ሌሊት ደህንነቶች በተደጋጋሚ በኃይልና በዛቻ እንደሚመረምሯቸው መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡ባለፈው የፍርድ ውሎ ታሳሪዎቹ ህጋዊ እውቅና ለተሰጠው ስብሰባ የቀሰቀሱ መሆኑን ጠቅሰው መታሰራቸው ህገ ወጥ በመሆኑ እንዲፈለቀቁ ቢከራከሩም፤ ፖሊስ ‹‹ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ስላልተያዙ መያዝ አለብን፡፡ እነሱም ከተለቀቁ መረጃ ያጠፉብናል›› በሚል የ7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተቀባይት አግኝቷል ለዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ አንድ ሳምንት ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዶለታል፡፡ በአንጻሩ ታሳዎቹ የቀረቧቸው ቅሬታዎችና መከራከሪያዎች ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡
10173740_613277408797921_4625849180036064757_n

 

ገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia

Hiber Radio: የአቶ ግርማ ሰይፉ ንግግር የአንድነት አቋም አይደለም ሲሉ አቶ በላይ ፈቃዱ ተናገሩ * ከለንደን ሶሪያ ሄዶ አሸባሪዎችን የተቀላቀለ አንድ ሀበሻ ተገደለ

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


ህብር ሬዲዮ ህዳር 14 ቀን 2007 ፕሮግራም !

<... ::>

የአንድነት ፕሬዝዳንት አቶ በላይ ፈቃዱ ሰሞኑን አንድነት የጀመረውን ዘመቻ፣ አቶ ግርማ ሰይፉ በተናገሩት ላይ፣ በምርጫውና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ከህብር ሬዲዮ ጋር ካደረጉት ቃለ ምልልስ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡ)

የኦባማ ኬር ዳግም ምዝገባና የአይ ኤር .ኤስ ቅታት ባልተመዘገቡት ላይ (ልዩ ቃለ መጠይቅ ከአቶ ተካ ከለለ በአትላንታ የቲኬ ሾው አዘጋጅ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ )

የአሜሪካ የምስጋና ቀንና የፕሬዝዳንቶቹ የምህረት ተግባር( ልዩ ዝግጅት ስለ ምስጋና ቀን)

ሌሎችም ዜናዎቻችን

አልሸባብ በኢትዮ ኬኒያ ድንበር ኦነግ በሚንቀሳቀስበት አካባቢ 28 ሙስሊም ያልሆኑ ሰላማዊ ሰዎችን ረሸነ።

ከለንደን ሶሪያ ሄዶ አሸባሪዎችን የተቀላቀለ አንድ ሀበሻ ተገደለ

የኢትዮጵያው አገዛዝ በዜጎች ኮምፒዩተር ላይ የሚያደርገውን ስለላ የሚያጋልጥና የሚያከሽፍ ሶፍት ዌር በነፃ መቅረቡን የመብት ተሟጋቾች ይፋ አደረጉ

የአንድነት ፕሬዝዳንት “አቶ ግርማ ሰይፉ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን አስመልክቶ የተናገሩት የፓርቲው አቋም አለመሆኑን” ገለፁ

አንድነት የፀረ ሽብር አዋጁን ተቀብሎ እንደማያውቅ ገለፀ

ፓርቲው የህሊናና የፖለቲካ እስረኞች ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ የሚጠይቅ ዘመቻ ጀመረ

በሰሜን ጎንደር ህዝቡ ተሰብስቦ በአገዛዙ ታጣቂዎች ሰሞኑን የተገደሉት ሰላማዊ ሰዎች ጉዳይ በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ ጠየቀ

በኢትዮጵያ በርካታ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በጫት ሱስ መለከፋቸውንና ጉዳዩም አሳሳቢ መሆኑ ተገለፀ

የኔቫዳ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሁበር ጉዳይ በተያዘው ፍ/ቤት ሊታይ እንደሚቻል ገልፆ የቀረበለትን ጥያቄ ውድቅ አደረገ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ


ሃገር ማለት –በሃብታሙ አያሌው (ሊያዩት የሚገባ)

የፕረዚዳንት ኦባማ የኢሚግረሽን ፖሊሲ ለውጥ

$
0
0

የ United States ፕረዚዳንት ባራክ ኦባማ ባለፈው ሐሙስ በሚልዮኖች የሚቆጠሩ የመኖርያ ፈቃድ የሌላቸው የውጭ ሀገር ተወላጆችን ህይወት ሊለውጥ የሚችል የ United States ን የኢሚግሬሽን ፖሊሲን የሚቀይር ውሳኔ እንደሚወስዱ ማስታወቃቸው ይታወሳል። አቶ ተመስገን ተካ የኢሞግረሽን ህግ ባለሙያ ያብራራስሉ።

አዳነች ፍሰሀየ
24.11.2014 23:41

ዋሽንግተን ዲሲ—
የ United States ፕረዚዳንት ባራክ ኦባማ ባለፈው ሐሙስ በሚልዮኖች የሚቆጠሩ የመኖርያ ፈቃድ የሌላቸው የውጭ ሀገር ተወላጆችን ህይወት ሊለውጥ የሚችል የ United States ን የኢሚግሬሽን ፖሊሲን የሚቀይር ውሳኔ እንደሚወስዱ ማስታወቃቸው ይታወሳል።

ይህ ፖሊሲ የሚመለከተው ከ 11 ሚልዮን በላይ ከሚሆኑት ህጋዊ የመኖርያ ፈቃድ የሌላቸው መጤዎች 5 ሚልዮኖቹን ነው። ውሳኔው በአብዛኛው የሚመለከተው ከላቲን አሜሪካ የመጡትን ቢሆንም ብዙ ኢትዮጵያውያንና ሌሎች አፍሪቃውያንም ተመሳሳይ ችግር እንዳለባቸው አሙን ነውና ስለ አጠቃላይ ይዘቱ እንዲያብራሩልን የኢሚግረሽን ህግ ባለሙያ የሆኑትን አቶ ተመስገን ተካን ጋብዘናል።

አቶ ተመስገን የአለም አቀፍ የንግድ ህግና የኢሚግረሽን ህግ ባለሙያ ናቸው።የአፍሪቃ ነክ ርእሶች አዘጋጅና አቀራቢ አዳነች ፍሰሀየ ናት ያነጋገረቻቸው። ውሳኔው የሚመለከተው የትኞቹን መጤዎች እንደሆነ በማብራራት ይጀምራሉ።

4F20E1B5-451B-4C29-B7A4-9FD9D7DCCE3D_w268_r1

ስለደፈራ፤ ደፈር ብለን ስናወራ (በእውቀቱ ስዩም)

$
0
0

ኣስገደዶ መድፈር በእንስሳት በኣሶች እንዲሁም በነፍሳት ኣለም ውስጥም ይስተዋላል፡፡ይልቁንም ለሰው እሩብ ጉዳይ በሆኑ ዝንጀሮዎች ዘንድ የተለመደ ነው፡፡ተፈጥሮ በደፋሪነት ያጨቻቸው ባብዛኛው ወንዶችን ቢሆንም ሞገደኛ እንስቶችም ኣልጠፉም፡፡ለምሳሌ ወንዱ ንብ ከሴቷ ጋር ሲሳረር ሴቲቱ በዚያ ነገር ቆልፋ ትይዝበታለች፡፡በጦዘ ስሜት ውስጥ ሆና ኣልመዝምዛ ትቆርጥበታለች፡፡ወይም በጅንኖች ኣባቶቻችን ኣነጋገር ትሰልበዋለች፡፡ኮርማው ንብ በጀንደረባነት የመቀጠል እድል የለውም፡፡ በደረሰበት ጥቃት ያልጋ ቁራኛ ማለቴ የቀፎ ቁራኛ ሆኖ ይሞታል፡፡ሰራተኛ ንቦች ኣስከሬኑን ከቀፎው ጠርገው ወደ ውጭ ይጥሉታል፡፡
ኣብሬሽ ኣድሬ ሲነጋ ልሙት
ላፈር ኣይደለም ወይ የተፈጠርኩት
የሚለው የሙሉቀን መለሰ ዘፈን የኮርማ ንቦችን ህይወት በደንብ ይገልጣል፡፡
Beweketu Seyoun joke about African leaders summit [Very Funny]
ኣስገደዶ መድፈር ባገራችን ትልቅ ጣጣ ሆኖ ይቆያል፡፡ምክንያቱም ወደ ጣጣው የሚያደርሱ ብዙ መንገዶች ኣሉ፡፡
ሲጀምር መናጢ ደሃ ነን። ሀብትና ስልጣኔ ባላቸው ሃገሮች የሴት ልጅን ዳሌ ላመል ያክል ነካ ካደረግህ ኣዳርህ ዘብጥያ ነው፡፡ኣገራችን ኢትዮጵያ ግን ቺስታ ናት ፡፡ያንድን ልጃገረድ መቀመጫ የሚጠብቅ የፖሊስ ግብረሃይል ማሰማራት የሚያስችል ሃቅም የላትም፡፡ሃቅም እንኳ ቢኖራት ባህሉ የላትም፡፡ የቤተመንግስቱን በር እንጂ ያንድን ሴት ገላ መጠበቅን እንደ ብሄራዊ ግዴታ የሚቆጥር ፖሊስ የለም፡፡
ባገራችን በዋናነት የሃብት ምንጭ ጉልበትና ህገወጥነት ነው፡፡ይባስ ብሎ፡ ባገሪቱ ውስጥ ያለው ሀብት ባብዛኛው በገልቱ ወንዶች እጅ ነው፡፡እኒህ ዲታ ወንዶች ድሃ ሴቶች ላይ ያሻቸውን ለማድረግ ኣቅም ኣላቸው፡፡ከሳሾችን ጸጥ የማሰኘት ጉልበት ኣላቸው፡፡የሀና ገዳዮች የተጋለጡት ወንጀላቸውን የሚሸሽጉበት ሃቅም ስለሌላቸው እንጅ እመቤት ፍትህ ፈጥኖ ደራሽ ስለሆነች ኣይደለም፡፡ተጠቅተው ያለ ኣለኝታ የቀሩትን ምኝታ ቤት ይቁጠራቸው፡፡
ሲቀጥል፤የትምርት ስርኣታችን ወንድ ኣንግስ ነው፡፡ሴት ልጅ የራሷ ነጻ ፍቃድ ያላት ፍጡር መሆኗን እያስረዳ የሚያንጽ የትምርት ስርአት የለንም፡፡ውጤቱ በእለት ተእለት ኣስተሳሰባችን ውስጥ ይታያል፡፡ብዙዎቻችን ሴቶችን” ሚስት እናት ገረድ” ከተባሉት መደቦች ባሻገር አናስባቸውም፡፡ኣዲስ ኣበባ ውስጥ ሴቶች ለሚይዟቸው መኪናዎች የሚሰጡ ስሞችን ኣስታውስ፡፡ኣንዷ መኪና” በእምሴ” ትባላለች፡፡ሴት በላቧ፤ጥራ ቆጥባ እቁብ ጥላ መኪና ልትገዛ ኣትችልም ከሚል ኣስተሳሰብ የመነጨ ስያሜን ነው፡፡
ኣንድ እውንተኛ ታሪክ እዚህ ላይ ላንሳ፡፡

ባገራችን መሚገኙ ከተሞች ባንዱ ውስጥ(ካርበኞች ጋር ኣላስፈላጊ ሙግት ውስጥ ላለመግባት የቦታውን ስም ዘልየዋለሁ)ኣንዲት ልጃገረድ በሰባት ጎረምሶች በፈረቃ ተደፈረች፡፡ይግረማችሁና ተኣምር በሚያሰኝ መንገድ ተረፈች፡፡ከህመሟ ኣገግማ መንቀሳቀስ ስትጀምር ግን ነዋሪዉ ኣለኝታነቱን ነፈጋት፡ኣንድ ቀን ከተማሪ ቤት ስትመለስ” ሰባት ጎራሽ” የሚል ስም ተወረወረባት፡፡ኣዲሱ ስሟ ከደፋሪዎች ይልቅ ተደፋሪዋን ባለጌ ኣድርጎ የሚያሳይ ነበር፡፡ቀስ በቀስ” ሰባት ጎራሽ” የሚለው ስም እንደ ተስቦ ተዛመተ፡፡ልጂቱ የሰባቱን ወንዶች ደፈራ መቋቋም ችላ ነበር፡፡ህብረተሰብ ተረባርቦ ሲደፍራት ግን ብርክ ያዛት፡፡ከእለታት ባንዱቀን ኣገር ለቅቃ ተሰደደች፡፡

አስገድዶ መድፈር ዋና መንስኤ የብልግና ፊልሞች መስፋፋት መሆኑን ገልጸው በፊልሞች ስርጭት ላይ ቁጥጥር እንዲደረግ የሚሰብኩ ኣሉ፡፡ይህን ምክር መቀበል አለመቀበል ስለሰው ተፈጥሮ ባለን አመለካከት ላይ የተመሰረተ ይመስለኛል፡፡ ሲመስለኝ፤ሰው ምናብ የሚባል ነገር ይዞ ከተፈጠረ ጊዜ ጀምሮ የብልግና ስእል ይፈጥራል፡፡የሆሊውድ ጠረን ከማይደርስበት እልም ያለ ገጠር ውስጥ ልጆች እንካስላንትያ ሲጫወቱ የሚያወጡት ብልግና እግዚኦ የሚያሰኝ ነው፡፡እኔና ኣብሮ ኣደጎቼ በልጅነታችን ሁለት ብልት ስላለው የቆሎ ተማሪ የሰማነው ተረት ከ ፕሌይ ቦይ መጽሄት የተቀዳ ኣልነበረም፡፡
በጥንታዊ የውትድርና ስርኣት ውስጥ ከመደበኛው ወታደር የተለየ፡ ሳይታዘዝ የሚዘምት የሰራዊት ዘርፍ ነበር፡፡ፋኖ ይባላል፡፡ዲሲፒሊን የማያውቅ ሀላፊነት የማይሰማው ከየት መጀመርና የት ላይ ማቆም እንዳለበት የማያውቅ ስድ ነው፡፡የሰው ኣእምሮም እንዲሁ ፋኖ ሀሳብ ያዘምታል፡፡ፋንታሲ ይሉታል ሳይኮሊጂስቶች፡፡ የብልግና ፊልሞችን ድርሰቶች የፋኖ ሀሳባችን ነጸብራቅ ናቸው፡፡ወደድንም ጠላንም ሰው የሚባለው ጣጠኛ ፍጡር እስካለ ድረስ ይኖራሉ፡፡ስለዚህ ሰዎች የሚያስቡትን ሁሉ ለማደረግ እንዳይሞክሩ ማሰልጠን እንጂ ሀሳባቸውን እንድያስወግዱ ማድረግ የሚቻል ኣይመስለኝም፡፡
ባንድ ወቅት በኣምስተርዳም ከማስረሻ ማሞ ጋር ስዞር የሰው ሰራሽ- ብልት መሸጫ ሱቅ ተመለከትሁ፡፡የመጀመርያው ስሜቴ ጉደኛው እግሬ ምን ኣይነት ቅሌታም ኣገር ላይ ጣለኝ የሚል ነበር፡፡ እየቆየሁ ሳስበው ሃሳቤን ለወጥሁ፡፡ባንድ ኣገር ውስጥ ያሉ ሰዎች ሁሉ በተፈጥሮ የሩካቤ ስሜት ኣላቸው፡፡ግን ሁሉም ወንድ ሴት የመጥበስ እድል የለውም፡፡ሁሏም ሴት በወንድ ደረት ላይ የመተኛት እድል ላይገጥማት ይችላል፡፡ዋናው እስኪገኝ ድረስ ባምሳሉ ከማዝገም ውጭ ምን ኣማራጭ ኣለ፡፡የተጠሙ ሰዎች እምቢባዮችን ኣስገደደው ለመርካት እንዳይነሳሱ ማገጃ ዘዴ ይሆን?

ባገራችን ብቸኛው የስነምግባር ምንጭ ሃይማኖት ነው፡፡የእምነትን በጎ ገጽ ግለሰቦችን ለመግራት ኣስፈላጊ ነው፡፡ያም ሆኖ ለእምነት ሃይሎች ያለን የተጋነነ ኣመኔታ የማታ የማታ ዋጋ የሚያስከፍለን ይመስለኛል፡፡ለምን? ምክንያቱ ግልጥ ነው፡፡የሃይማኖት ኣባቶች የመኖራቸውን ያክል የሃይማኖት እበቶችም በየቦታው ኣሉ፡፡
በዚህ ጉዳይ ኣንድ ሁለት ተምሳሌቶችን ጠቅሼ ዞር ልበል፡፡

የመከራ ቀንበሩን ያቅልለትና ተመስገን ደሳለኝ ከእስር ቆይታዎቹ ባንዱ ከሁለት ሽሜ እስረኞች ጋር ተገጣጥሞ ነበር፣ የመጀመርያው ስድስት ኣመት ህጻን የደፈሩ ሼህ ሲሆኑ፡ ሁለተኛው ብልታቸውን ማር በመቀባት ህጻናትን ሲያጠቡ የተገኙ መርጌታ ናቸው፡፡የመርጌታን ስልት የፈረንሳዩ ወፈፌ ማርኬስ ደ ሳድ እንኳ የደረሰበት አልመሰለኝም፡፡
ኣዲስ ጉዳይ መጽሄት ባንድ ወቅት በወንጀል ኣምዱ ኣንድ ታሪክ ኣስነብቦ ነበር፡፡ታሪኩን ኣሳጥሬ ስተርከው የሚከተለውን ይመስላል፡፡ሰውየው ፓሰተር ነኝ ብሎ ካንድ ቤተሰብ ጋር ይተዋወቃል፡፡ጥቂት ሳይቆይ ከመላው ቤተሰብ መካከል ልጃገረዶቹን መርጦ ጸለየላቸው፡፡ ከዚያም ሶፍት ዌር ይመስል እጄን ካልጫንኩባችሁ ኣላቸው፡፡ከጥቂት ጊዜ በሁዋላ የሰራ ኣከላቱን ጫነባቸው፡፡ፖሊስ ጫኝና ኣውራጁን ፓስተር በቁጥጥር ስር ባዋለበት ወቅት ከተደፈሩት ሴቶች መካከል ኣንዷ ራሷን ሰቅላ ነበር፡፡

በመጨረሻም
በየትኛውም ማህበረሰብ ውስጥ ምክር የማያለዝባቸው፣ ትምርት የማይቀይራቸው ጉዶች ይኖራሉ፡፡የተሻለው መንገድ ልጆቻችንን የኒህ ጉዶች ሙርጥ የማይደርስበት ቦታ ላይ መቀመጣቸውን ማረጋገጥ ነው፡፡ወላጅ የማያንቀላፋ የልጆቹ እረኛ መሆን ግዴታው ነው፡፡

የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በፖስታ የተላከውን የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ደብዳቤ አልቀበልም አለ

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) የአዲስ አበባ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል 9ኙ ፓርቲዎች ህዳር 21 ለሚያደርጉት የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በፖስታ ቤት የተላከለትን ደብዳቤ አልቀበልም ማለቱን የስብሰባው አስተባባሪ የሆነው የመኢዴፓ ፀሀፊ አቶ ዘመኑ ሞላ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
postal service ethiopia
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 21/2007 ዓ.ም ለሚያደርጉትና መኢዴፓ ለሚያስተባብረው ስብሰባ ረቡዕ ህዳር 10 የመኢዴፓ አመራሮች ደብዳቤውን ለማስገባት ሄደው የነበር ቢሆንም አቶ ማርቆስ ብዙነህ እና እሳቸውን ተክተው ሲሰሩ የነበሩት አቶ ፈለቀ ታመዋል በሚል የከንቲባ ጉዳይ የካቢኔዎች ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው ማሳወቂያ ደብዳቤውን አንቀበልም ማለታቸው ይታወቃል፡፡

በተመሳሳይ ህዳር 12 ወደ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍሉ ያቀኑት የትብብሩ አመራሮች ደብዳቤውን የሚቀበላቸው ሲያጡ ጠረጴዛ ላይ ጥለውት የመጡ ሲሆን በፖስታ ቤት በሪኮመንዴ eg156846735et እንደላኩ የትብብሩን ፀኃፊ አቶ ግርማ በቀለን ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ለአዲስ አበባ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በፖስታ የተላከውን ደብዳቤ ቢደርስም አመራሮቹና ሰራተኞቹ ደብዳቤውን ለመቀበል ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ፖስታ ቤት ድረስ በመሄድ እንዳረጋገጡ አቶ ዘመኑ ሞላ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ሰራተኞችና አመራሮች ፖስተኛው ደብዳቤው የሚሰጥበትን ቢሮ ሲጠይቅ ለማሳየት ፈቃደና እንዳልሆኑና በስተመጨረሻም ‹‹ተቀባይ የለውም ብለህ መለስ፡፡›› እንደተባሉት አቶ ዘመኑ ሞላ ገልጸዋል፡፡

አሸባሪ አለ። እሱም መንግስታችሁ ነው። (ዳዊት ዳባ)

$
0
0

ጦርነትትን ሰርተን ድል እናመጣለን የሚለው  ስልጣን ላይ ያላው አካል አይዶሎጂ እንደሆነ  ይታወቃል። ቦንብ አፈንድቶ ንፁሀን ዜጎችን ፈጅቶ የስልጣን እድሜን ለማራዘም በብዙ አኳያ ሲጠቀሙበት እንደነበረም የሚታዋቅ ነው። ያገራቸውን ሁኔታ በቅርበት የሚከታታለ ዜጎች መንግስት ያደርጋል ብሎ ለማመን ቢከብድም  ለመናገር የማይቻልበት ሁኔታ ውስጥ ባይሆኑም ይህን ማወቅ ግን  ነበረባቸው።   ቦንብ እያፈነዱ ብዙ ጊዜ አስርና አምስት ንፁሀን ዜጎች ተቀጥፈዋል። ታዲያ የከበደን የትኛው ለማመን የሚከብድ ሆኖ ነው?። ጢቢ ጢቢ እንደሚጫወቱበት ህዝብ በእምነቱ ወይ በዘሩ ጎራ ለይቶ ፀብ ውስጥ ቢገባስ ኖሮ?። አሪዬሳዊ በሆነው በዚህ ተግባራቸው አይደለም  እሳት እዚህና እዚህ ብልጭ ድርግም ሲል እያየን ያለነው?። እንቅልፍ የሚነሳን እንድ ቀን ስንነሳ የሰደድ እሳት እንደሚሆን ማወቃችን አይደለም ወይ።  ቦንበኛነቱን ለወደፊቱም የተበላ ነው ብለው ይተውታል ማለት ባልችልም እየተረቀቁበት ግን ሄደዋል። አሁን አሁን ህግ እያመረቱ   ቦንብ እያፈነዱ ሲጠቀሙበት ለነበረ ጉዳይ እየተጠቀሙበት ነው?። ህጎቹ የተመረቱትም አንድና አንድ ለዚሁ አላማ ነው። ይህን ስለምናውቅ መሰሎኝ አምርረን የምንቃወመው።

ከዚህ መረዳት ተነስቼ አቶ ግርማ ሰይፉ በማክበር ተሳስተዋል። ስህተት የሆኑት በዚህ ህግ ሽብርተኛ ተብለው የታሰሩትን ዜጎችን ሁሉ የታሰሩበትን ጉዳይ ሁሉ ባያውቁም ማወቅም ባይጠበቅቦትም መንግስት ነኝ የሚለውንና እየታገሉት ያሉትን አካል ማወቅ ስለነበረቦት ነው። ቁጣ ያስነሳው የሚመስለኝ በዚህ ደረጃ የሚያውቁት ብዙዎች መሆናቸው ነው። እርሶም ያውቃሉ የሚል ግምት ስለነበረ ነው። ባጭሩ ንግግሮት ከኢትዬጵያ ውጪ የትም አገር ላይ አንድ ሰው ተናግሮት ቢሆን ሚዛናዊ ያሰኝው ነበር።  በኛ ሁኔታ ግን ሀናን ማን ሺሻ ቤት ሂጂ አላት ብሎ እንደመውቀስ መሰለ። ለመጨመር አላማው ህዘብን ማሸበር ሲሆን እንጂ ቦንብ ማፈንዳት ሁሉ አሸባሪነት ነው ያለው ማነው። እኔም እንኳ ብችል አናታቸው ላይ እበትነው ነበር።

ያም ሆኖ መካበድ አለበት ወይ?። የሚካባድ ነገር የለውም። አቶ ግርማ ቆራጥ ታጋይ ነው ወይ? አንበሳ ታጋይ ነው። ወያኔ ነው ወይ?። ወያኔዎች ናቸው የሚሉት። ከአንድነት ፓርቲ ጋር ይያዛል ወይ?። ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ምን እንደሆነ ካላወቅን አዎ። አንድነት ምርጫ ለመሳተፍ ከመወሰኑ ጋር ይገናኛል ወይ? በየትም በኩል።

ሌላው የይቅርታ ጉዳይ እኛ ፖለቲካ ውስጥ በተነሳ ቁጥር ያመኛል።  መጀመርያ ይቅርታ ማለት አለበት። ወይ አለባቸው። በሗላ ሂሳብ እናወራርዳለን።ነብሴ ነው። ይቅርታ በለ ወይ በይ ሞቼ ነው። ብቻ ጠያቂውም እንቢ ባዩም ብዛቱ። ሁላችንም ሁሌም ማስታወስ የሚገባን ሰቃዬቹ አይደሉም እየሱስ ክርስቶስ ነው ፈቅዶ ይቅርታ ያለው።

ከማቆሜ በፊት ለዚህ ሁሉ ተጠያቂ የማደርገው አቶ ግርማ ሰይፉን አይደለም ግርማ ካሳን ነው። በተደጋጋሚ አይቼሀለው ለኳሽም ገላጋይም መስለህ ትሰራለህ። በቅርብ ባወጣህው ፅሁፍ አገዛዙ ግንቦት ሰባት እየለ ግፍ የሚፈፅማቸውን ዜጎች ታግሎ ላይታግል ደባ በሚመስል ጥፋቱ የግንቦት ሰባትና በእርግጥም ከታሰሩት ውስጥ አባል የነበሩ እንዳለ ፅፈሀል። ይህን ሀሳብ ወደህዝብ የገፋህበትን መረጃ አቅርብ። ማቅረብ ካልቻልክ መፃፍ አቁም። ለመከልከል ሳይሆን ተንኮልህ ይቆማል።  ቲካ ቲካውንና መቀጠሉን ስለምትወደው ለመዝጋት የአርዬሶቹን  ወይ የአርቲስት ደበበ እሸቱን ግፍ ያየንበትን ቪዲዬ አይነት መረጃ ግን ተቀባይነት የለውም።

ለማንኛውም ለመንበዛበዝ ጊዜ የለንም ወደፊት።

ዳዊት ዳባ

Comment

 

 

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live