Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ስልጣኔን የለቀኩት በአንዳንድ ብልጣብልጦች እና የሴራና አድማ አካሄድ በሚችሉ ሰዎች ፓርቲው ስለተጠለፈ ነው

$
0
0

“ስልጣኔን የለቀኩት በአንዳንድ ብልጣብልጦች እና የሴራና አድማ አካሄድ በሚችሉ ሰዎች ፓርቲው ስለተጠለፈ ነው::’ – አቶ አበባው መሓሪ የመኢአድ ፕሬዚዳንት

“ፓርቲው ወደፊት ለመራመድ የማይችልበት ወደፊትም የማይሻሻልበት ደረጃ ላይ ደርሷል::”አቶ አበባው
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
Abebawየመኢአድ ፕረዚዳንት የነበሩት አቶ አበባው መሓሪ ስልጣናቸውን ሊለቁ የቻሉት በገጠማቸው አስገዳጅ የድርጅታዊ የውስጥ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል እንደ አቶ አበባው ደብዳቤ በአብዛኛው የመኢአድ አባላት ከፍተኛ የድምጽ ድጋፍ ከተመረጥኩበት የፕሬዚዳንትነት ቦታ ላይ ድርጅቱ ወደፊት እንዳይራመድ የሚያደርጉ እና ከዚህ በፊት ተሳስረውና ተቆላልፈው በመጡ የውስጥ ችግሮች ለሃገራቸው መስራት አለመቻላቸውን በመጥቀስ ፓርቲው ወደፊት የማይራመድበት አጣብቂኝ ውስጥ መሆኑን ለጠቅላላው ጉባዬ ገልጸዋል::የመኢአድ የውስጥ ችግር በመጪው የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ላይ ውሃ የቸለሰ ነው ያሉት አቶ አበባው ኢትዮጵያውያን አቤት የሚልላቸው አካል እየጎደለ መሄዱን ጠቁመው በመኢአድ ውስጥ ያለው ችግር ከአቅም በላይ የሆነ ስለሆነ ፍርዱን እና መዝገቡን ለታሪክ በመተው ስልጣናቸውን እንደለቀቁት ከአቅም በላይም እንደሆነ አስረድተዋል::

ከአቅም በላይ ያሉትን ጉዳይ ሲገልጹ … ለየኢትዮጵያውያን ምሁራን ከትግሉ መሸሽ ምክንያቱ የትግሉ መስመር በአንዳንድ ብልጣ ብልጦች እና የሴራ እና የአድማ አካሄድን በሚችሉ ግለሰቦች ስለሚተለፍ መሆኑን መኢአድ ውስጥ ከተከሰተው ችግር እንደተገነዘቡ በደብዳቤያቸው ገልጸዋል::

የአቶ አበባው መሃሪ ፊርማ የሰፈረበትን ሙሉ ደብዳቤውን ከታች ያንብቡት :

10806462_875292445814912_7187866189333442964_n
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

– See more at: http://satenaw.com/amharic/?p=2462#sthash.hzTc9P9Y.dpuf


በድሬዳዋ ዩኒቪርሲቲ የሚማሩ የአፋር ተማሪዎችን ባህላዊ ወይም ሃይማኖታዊ ልብስ እንዳይለብሱ ተከለከሉ

$
0
0

አኩ ኢብን አፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው

ተማሪዎቹ እንደሚሉት ከሆነ በመመገቢያ ሬስቶራንትና ላይብረሪን ጨምሮ የባህል ልብስ ማለትም ሽሪጥና የመሳሰሉትን የባህል ልብስ መልበስ አትችሉም እንደሚባሉ በምሬት ገልፀዋል።

afar womenበኢትዮጵያ ህገ መንግስት የባህል፣የሃይማኖትና የብሄር እኩልነት አረጋግጠናል ይላል ግን ወያኔ የሚመራው የኢህአዴግ ፓርቲ በተግባር ላይ ማሳየት አልቻለም ይላሉ።

ከሁሉም በላይ ግን ይላሉ ተማሪዎች ያሳሰበን የሃይማኖት ጉዳይ ነው።

ሶላት ልንሰግድ የሚፈቅድልን ሃይማኖታችን በሚፈቅደው መልክ ሳይሆን ኢህአዴግ በሚፈልገው መልክ ነው።

ሶላት የምንሰግድበት ሰዓት ላይ ያስተምሩናል።

ሶላት እንደ ሃይማኖት አያዩትም አስፈቅደህ ሰግደህ ልትመለስ የማይታሰብ ነው።

ብንሰግድም በጀማኣ ወይም ተሰብስበን አብረን መስገድ አንችልም።

ስለዚህ አባቶቻችን በዲን (ሃይማኖት)ና በባህል መደራደር ሰላልስተማሩን ጉዳዩ በጣም አሳስቦናል ብሏል።
የአፋር ሙስሊም ተማሪዎች ቁጥር መጨመር ያልወደደው የወያኔ መንግስት በዩኒቨርስቲዎች ላይ ከፍተኛ እንግልት እያደረሰባቸው ይገኛል።

“ከዚህ በፊት ከባህርዳር ዩኒቨርስቲ ብዙ የሙስሊም ተማሪዎች መባረራቸው የሚታወስ ሲሆን ከተባረሩት ውስጥ ብዙዎቹ የአፋር ተማሪዎች መሆናቸው ይታወቃል። በተለያዪ ዩኒቨርስቲዎች የአፋር ሙስሊም ተማሪዎችን ለማስፈራራትና ለማሸማቀቅ የተለያዩ ስልቶችን እየተጠቀሙ ይገኛሉ። ሰሞኑን በድሬ ዳዋ ዩኒቨርስቲ ውስጥ የባህልና ሃይማኖታዊ ልብስ እንዳይለብሱ መከልከል መጀመሩ የዚሁ ሴራ አካል ነው ። በአሁኑ ሰዓት በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ 59 የአፋር ተማሪዎች እየተማሩ ይገኛሉ የሚሉ” የፖለቲካ ታዛቢዎች አሉ::

ፍልፍሉ አሜሪካ እንዳይገባ ተከለከለ

$
0
0

በምነው ሸዋ ኢንተርቴይመንት በኩል ወደ ሰሜን አሜሪካ መጥቶ የነበረውና በተለያዩ ስቴቶች የኮሜዲ ሥራዎችን ቢያቀርብም ብዙም ተቀባይነት ሳያገኝ ወደ ሀገር ቤት የተመለሰው ኮሜዲያን ፍልፍሉ ተመልሶ ወደ አሜሪካ ለመምጣት ፈቃድ ቢጠይቅም በአሜሪካ ኤምባሲ በኩል መከለክሉ ታወቀ::
filfilu
ኮሜዲያኑ ወደ ሃገር ቤት እመለስበታለሁ ብሎ ለኢምባሲው ከተናገረበት ቀን በጣም አሳልፎ ወደ ሃገር ቤት በመመለሱ የተነሳ አሁን በድጋሚ ወደ አሜሪካ የመግቢያ ፈቃድ ሲጠይቅ ተከልክሏል:: ፍልፍሉ በስሜን አሜሪካ በተዘዋወረባቸው ከተሞች በኮሜዲ ዝግጅቶቹ ላይ የተጠበቀው ያህል ሰው ያልተገኘ ሲሆን በርካታ ፕሮሞተሮችም ለኪሳራ መዳረጋቸውን በተለያዩ አጋጣሚዎች ሲገልጹ ይሰማል::

ፍልፍሉ ለመድረክ ስራዎች ሳይሆን ለተቀረጹ ስራዎች ብቻ የሚሆን ኮሜዲያን ነው የሚሉት ለሙያው ቀረብ ያሉ ሰዎች ያልፈጠረበትን ስታንዳፕ ኮሜዲ አቀርባለሁ ብሎ ለትዝብት መውደቁን ይናገራሉ::

ኮሜዲያን ፍልፍሉ የባለስልጣን ልጅ አግብቼ ቤተሰቦቿ ኢትዮጵያ ውስጥ ሊገሉኝ ይፈልጋሉ እያለ በሰሜን አሜሪካ ቆይታው ሲናገር የቆየ ሲሆን ሃገር ቤት እንደገባም በዱሪዬዎች መደብደቡ አይዘነጋም::

ኮሜዲያን ፍልፍሉ ወይም በረከት በቀለ የአሜሪካ መግቢያ ፈቃድ ከተከለከለ በኋላ በየሚዲያው በመቅረብና በሄደበት ቦታ ሁሉ አሜሪካንን በማጥላላት ላይ እንደሚገኝም ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለክታል::

አዲሱ የመኢአድ አመራር ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር የተጀመረው ግንኙነት እንደሚያስቀጥል አስታወቀ

$
0
0

• የፓርቲውን ማህተም ተሰርቄያለሁ ብሏል

aeupዛሬ ህዳር 4/2007 ዓ.ም በፓርቲው ዋና ጽፈት ቤት መግለጫ የሰጠው የመኢአድ አዲሱ አመራር ከመኢአድ ጋር ተመሳሳይ ፕሮግራም ካላቸውና ከሌሎቹም የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ከአሁን ቀደም አብሮ ለመስራት የተጀመረውን እንቅስቃሴ እንደሚያስቀጥል አስታውቋል፡፡

በ2003 ዓ.ም ከታህሳስ 15-17 ድረስ አይቤክ ሆቴል ጠቅላላ ጉባኤ ከተካሄደ በኋላ በፓርቲው አመራሮች መካከል ችግር እንደነበር የገለጸው አዲሱ አመራር ከዛ በኋላ አቶ አበባው መሃሪ ፕሬዝደንት የሆኑበት አካሄድ ትክክል እንዳልነበር፤ለአራት አመት ያህል በሁለቱ ቡድን መካከል የነበረው አለመግባባት በእርቅ እንደተቋጨና አቶ አበባው ኃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው እንደለቀቁ የጻፉትን ደብዳቤ ዋቢ አድርጎ ገልጾአል፡፡ በመሆኑም የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ያለ ምንም ገደብ ወደ መኢአድ ጽ/ቤት መምጣት ይችላሉ ሲል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

በአንጻሩ አዲሱ አመራር በህገ ወጥ መንገድ ነው ወደ ስልጣን የመጣው በሚል ቅር የተሰኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ዛሬ ከሰዓት መግለጫ እንደሚሰጡ ተሰምቷል፡፡ ጉዳዩን ለማጣራት አቶ አበባው መሃሪ ጋር በተደጋጋሚ ብንደውልም የእጅ ስልካቸውን ሊያነሱ ባለመቻላቸው ሀሳባቸውን ማጠቃለል አልቻልንም፡፡

በሌላ በኩል አዲስ አመራር ማህተሙ አዲሱ አመራር ከመምጣቱ በፊት ፓርቲው ውስጥ በነበሩትና በአዲሱ አመራር ጋር ባልተስማሙ አካላት እንደተሰረቀ አስታውቋል፡፡ ‹‹ማህተሙ ከዚህ ቤት በነበሩ ሰዎች ተሰርቋል፡፡ ይህን ጉዳይ በወቅቱ ለፖሊስ አመልክተናል፡፡ በፓርቲው ማህተም እኛ የማናምንበትና ህገ ወጥ ነገር ቢሰራበት ተጠያቂ የሚሆኑት እነሱ ናቸው፡፡›› ሲሉ አዲሱ የፓርቲው ፕሬዝደንት አቶ ማሙሸት አማረ ገልጸዋል፡፡

ብርቱካን በሊባኖስ ተረፈች ፣ አልማዝ በኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ቀረች ! የተረፈችው የእህት ብርቱካን ጉዳይ …(ነቢዩ ሲራክ)

$
0
0

birtukan

የማለዳ ወግ …
ብርቱካን በሊባኖስ ተረፈች ፣
አልማዝ በኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ቀረች !

የተረፈችው የእህት ብርቱካን ጉዳይ …

በሃገረ ሊባኖሰ ቤሩት  ከ4ኛ ፎቅ ወድቃ የተረፈችው እህት ብርቱካን  ጤንነት የተስተካከለና ከድካም ህመሟ ሙሉ በሙሉ እያገገመች መሆኑን መረጃዎች ማምሻውን ደርሰውኛል ። የቆንስል ሃላፊዎች አልማዝን ሲያነጋግሯት በሊባኖስ ቆይታ ስራ መስራት እንጅ ወደ ሀገር ቤት መመለስ እንደማትፈልግ እንደገለጸችላቸው አምባሳደር ሐሊማ ሙሃመድ አጫውተውኛል። በቀጣይ ቀናትም ህክምና እየወሰደች ያለችበትን መካስድ ሆስፒታልን ለቃ እንደምትወጣ ፣ በቤሩት የቆንስል መጠለያ ሆና ህክምናና ጉዳይዋን እንደምትከታተል ተረድቻለሁ !

ተስፋ የቆረጡት ኢትዮጵያውያን አስተያየት …

    በብርቱካን ጉዳይ ዙሪያ ያነጋገርኳቸው ብዙ ነዋሪዎች የቆንስል ተዋካዮች ላይ እምነት እንደሌላቸው ይገልጻሉ ። እንደ አማራጭም የብርቱካንን ጉዳይ በጠበቃ አስይዘው ለመከራከር የሚቻልበትን ንገድ ለማፈላለግ ስራ መሰራት አለበት ሲሉ  ” የቆንስል ሃላፊዎችን ዲስኩር ማመን ትቶ የተለመደው የነዋሪውን ትብብር ማስተባበር ያሻል ” ይላሉ።  ለምን በመንግስት ተወካዮቻችን እምነት አጣችሁ?  ማለቴ አልቀረም ፣ ምላሻቸው ዘርዘር ያለ መረጃና ማስረጃ ያለው እውነት ይመስላል። አንድ ያሉኝን ብቻ ላንሳው  … በሃገራ ባንዴራ ስር ፣ በቆንስሏ በር በጥጋበኛ “ጀብራሬ” አረብ  እየተጎተተች ስትደበደብ የቆንስል ሀላፊዎች ምንም አለማድረጋቸው ፣  ከዚያም  ሃኪም ቤት በገባች በቀናት ልዩነት ” ራሷን በራሷ ገደለች !” መርዶ ነጋሪና ሬሳ ተቀባይና ላኪ ከመሆን ያለፈ ስራ የመብት ማስጠበቅ ስራ በቆንስል መስሪያ ቤቱ አለመሰራቱን ያጣቅሳሉ።  ከዚሁ ጋር በተዛማጅ ከአንድ ወር በፊት እዚያው ሊባኖስ “የአሰሪዋን ህጻን ልጅ አፍና ገድላለች! ” በሚል በፍርድ ውሳኔ ያልተሰጠው ጉዳይ በመገናኛ ብዙሃን ቀርቦ ነበር። በቀረበው መረጃ ስማችን ጎደፈ ። ዳሩ ግን የቀረበው መረጃ ኢትዮጵያዊቷ ወንጀለኛ አለመሆኗ ፍንጭ ሰጠ ፣ የራሳቸው ዜጎች ከሳሽ ባቀረበው መረጃና ማስረጃ ተመርኩዘው የተገላቢጦሹን አሳዩት ። ይህ ሁሉ ሲሆን የመንግስት ተወካዮቻችን ከሳሽን ወደ ተከሳሽነት የሚያሸጋግረውን መረጃ እንኳ ይዘው ታሳሪዋ ኢትዮጵያዊት እህት በዋስ መብቷ  ተጠብቆ በውጭ ሆና  እንድትከራከር አለማድረጋቸው በቆንስሉ የብርቱካን ክትትል ላይ የረባ ውጤት የማምጣት አቅም እንደሌላቸው ማሳያ ነው በማለት የሰላ ሂስና ወቀሳ ያቀርባሉ ።

የተስፈኞቹ ኢትዮጵያውያን አስተያየት …

    ” በቤሩት የቆንስል መ/ቤት ከበፊቱ የተሻለ ለውጥ ይታያል! ”  ያሉኝ ወገኖች ፣ ለውጥ ለመምጣቱና ለመታየቱ የሚያቀርቧቸው ጥቃቅን የቆንስል ግልጋሎት አሰጣጥ መረጃዎች ናቸው ።  ያም ሆኖ የመስራት አቅሙ የላቸውም ያሉኝ  የሚያነሱትን ” …የከዚህ በፊቱን የአለም ደቻሳና ሌላው ሌላው አሳዛኝ የመብት ጥበቃ ጉድለት “ያለፈው አለፈ ፣ ይሁን !”  ቢባል አሁን ድረስ እንዳልተሻሻሉ ብዙ ማሳያ አለ። ከወር በፊት  በነፍስ ግድያ ወንጀል ያለ ተጨባጭ መረጃ የታሰረችውን እህት ቆንስሉ አያማክሯትም ። ለዋስ መብቷን አላስጠበቁላትም።  ” በማለት “የቀረበውን የሰላ ሂስ ” ለውጥ አለ! ” ባዮች በተጨበጠ መከራከሪያ መላሽ ለመስጠት አልተቻላቸውም ።  ብቻ የቀረበውን ወቀሳ ሳያስተባብሉ ” በለውጥ ተስፋ ከማድረግ የተሻለ ነገር የለም! ”  በማለት የቆንሰል መ/ቤቱ የብርቱካንን ጉዳይ በቅርብ ተካታትሎ ውል እንደሚያስይዘው ያላቸውን ተስፋ አጋርተውኛል  !  …ቀጣዩ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ቢቸግርም ዛሬ የእህት ብርቱካንን በአሰቃቂ ሁኔታ መውደቅና ከከፋ አደጋ መትረፏ በሊባኖስ ቤሩት ካሉት ባለፈ በአለም ዙሪያ ሆነን ጉዳዩን በቅርብ ለተከታተልን ሁሉ እፎይታ ሆኗል  … ተመስገን ነው !  እናም ” ያገባናል ” ባዮች በእህት ብርቱካን ሰናይ ዜና ተደስተን ፊታችን ወደ ሌላዋ ግፉዕ ማዞር ግድ ብሎን  ወደ አልማዝን እንርዳ ” ዘመቻችን ፊታችን መዞራችን እውነት ነው!

የአካል ጉዳተኛዋ የአልማዝ ጉዳይ  …

   ህዳር 2 ቀን 2007 ምሽት በሊባኖስ  የብርቱካንን ከፎቅ መውደቅ አሳዛኝ ዜና ስሰማ በሌላኛው አረብ ሀገር በኦማን የመኪና አደጋ ደርሶባት የአካል ጉዳተኛ በሆነችው በእህት አልማዝ ጉዳይ ተወጥሬ ነበር።  ከተለያዩ አረብ ሃገራት እና በሃገር ቤት በማህበራዊ መገናኛዎች ተገናኝተን የተውጣጣን ወደ ስድስት የምንደርስ ወንድምና እህቶች  ባንድ እየመከርን ነው። አላማችን ከመረጃ ልውውጡ ባለፈ የወገናችን እንባ በተግባር መጥረጉም “ያገባናል !” ብለን ነው። የእህት አልማዝን እርዳታ ለማሳካት ማድረግ ስላለብን ጉዳይ እየመከርን ባለበት ወቅት ከቤሩት የብርቱካን አደጋና  “አትተርፍም!” የተባለ መረጃ ደረሰኝ … ሌላዋን የአረብ ሃገር ኦማን ጉስቁል እህት አልማዝን አሰብኳት …

    እህት አልማዝ የአረብ ሃገሩ ስደት ሲነሳ ከመንግስት ጀምሮ እስከ ግለሰብ የእኛ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆነ ድጋፍ እህቶቻችን አደጋ ላይ ጥሏቸዋል።በህግ ሽፋን ተሰጥቷቸው በሚንቀሳቀሱ ወሮበላ ህግ ይጣሳል ፣  ለህዝብ ቆመናል በሚሉ የመንግስት ተቋማት ህግ ይጣሳል ፣  በመልካም አስተዳደር እጦት ፣ በሙስና  ህይወታችን ከፍቷል ፣ በተለያያየ መንገድ በአረበወ ሃገራት ለገነነው “ዘመናዊ ባርነት ” ድጋፍ እያደረግን እያበረታታን ነው ። ይህን ማለቴ ያለነገር አይደለም ፣ በአረቡ ሃገር በኦማን አካሏ ተሰናክሎ  የእኛን እርዳታ ጠባቂ የሆነችውን እህት አልማዝ አበሳ አስታውሼ ብዙውን አውጥቸ አወረድኩት …

    …አልማዝ አንድ ፍሬ ጉብል ሳለች ካላቻ ጋብቻ   ትዳርን ሳታውቀው መስርታ ልጅ ወልዳ ነበር ፣ ብዙም ሳይቆይ ጉብሏ እናት ሆነች ፣  ኑሮ አልሞላ አልሳካ ብሏት ወደ አረብ ሀገር ወደ ኦማን ተሰደደች … ሙሉ አካሏን ይዛ ለስራ ብላ በራ ከሄደችበት ኦማን ሞስካት ብዙም ሳትቆይ ለመኪና አደጋ ተጋለጠች ፣  ሆስፒታል ገባች ፣ ለወራት በህክምና ስትረዳ ብትቆይም አዕምሮዋ ፣ እግሯና እጇ ብሎም መላ አካሏ የከፋ ጉዳት ደረሰባቸው ፣ አይሆኑ ሆነች: (  ከሃገር ቤት ጀምሮ በአረብ ሀገራት ብርቱ መረብ ያላቸው ደላሎች እህት አልማዝ ሆስፒታል ከገባች በኋላም በጉዳቷ ለመጠቀም መስገብገባቸውን ጠልቆ መረጃ መሰብሰብ አሞኛል ፣ ዛሬ ወደ ክፉዎች ባለ ጊዜ ደላላ ባለጸጎች መሰሪ ምግባር ዳሰሳ አልገባም !  … እህት አልማዝ በተስፋ አቢሲኒያ በጎ አድራጊ ቡድን  አባላት ፣ በተለይም በመስራቹ ብርቱ ወንድም በወዳጀ በመሳይ አክሊሉ ( በኑቢያ ኩሽ ቀዳማዊ  ) እና በወዳጆቹ ብርታት  በአሳር በመከራ ሃገር ቤት ገብታለች ። መቄዶንያ የአረጋውያን ደጋፊ በጎ አድራጊ ቡድን ትብብርም መጠለያም ተሰጥቷታል ።  … እህት አልማዝ እዚህ ላይ ደርሳለች …  ይህም ተመስገን ነው!

   ይህም ሁሉ ሆኖ የአልጋ ቁራኛ የሆነችው አልማዝ ” ከህመም ጉዳቷ የምታገግምበት ተስፋ አለ ” በመባሉ የእርዳታ ስራ ተጀምሯል ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ በተጀመረው እርዳታ እዚህ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ያለውን እርዳታ ለማስተባበር ሃላፊነት ከወሰድኩ ቀናት ወዲህ ወገኖች አልማዝን ለመርዳት ያሳዪት መነቃቃት እጅግ በጣም አበረታች ሆኖ ቀጥሏል። በኮንትራት ስራ በየአረቡ ቤት የሚሰሩ እህቶቸ የ “ነግ በኔ ” ብለው በሰብአዊነት እያደረጉት ያለው መተባበር ውስጥን ስሜት የሚያረካ ለመሆኑ እማኝ ለመሆን ታድያለሁ  !  የቤት ቆሻሻ ለመጣል መውጫ ቀዳዳውን ፈልገው ያላቸውን ለአልማዝ ለማካፈል ያሳዩት ቅንነት ፍጹም በቃላት ልገለጽ የማይቻለኝን ኩራት፣ በእህቶቼ እንድጎናጸፈው ዘንድ  ምክንያት ሆኖኛል  ! ድምጻዊ  ጆሲ እንደ ሀውስ ያን ሰሞን እርዳታ ለማሰባሰብ ሲሞክር በገጠመውና በሆነው በግኖ ይመስለኛል   ” ለመስጠት መሰጠት ያስፈልጋል! ”  ማለቱ በእኔም ላይ ደርሶ  እውነት ነው ብያለሁ  ! ለእኔ እርዳታ ማድረግ ትርጉሙ ገንዘብ መስጠት ብቻ አይደለም ፣ ቀና ማሰብ ፣ መረጃ መለዋወጥ ፣ ሌላ ተዛማች ተጎጅውን የሚደግፍ ስራ መስራት ፣ የሚረዳን አለመቃወም ፣ ገንዘብ  ከመስጠት ባለፈ ለተጎጅው ወገን ወገናዊ አብሮነት  ፍቅር መግለጫ ነው… ባይ ነኝ  !

    ለማንኛውም ብርቱካን በሊባኖስ ተረፈች ፣ እሰየው ነው!   እህት አልማዝ በኦማን ተሰናክላ እንዳትቀር ወገናዊ ትብብራችን ትሻለችና እናስብበት !  በዚህ የበጎነት መንገድ በመጓዝ በጠና የተጎዱ ወገኖቻችን  በመደገፍ ልንታደጋቸው ካልቻልን ከንፈር መምጠጡ ብቻ እንዳላዋጣን ከእኛ በላይ የሚያውቀው የለም ! እናም የዜጎቹን መብት እንዲያስከብር መንግስትን ስንወተውት የዝሆን ጀሮ ሰጥቶ አልሰማን ቢልም ጩኸት በደላችን እስኪሰማ እየጮህንም ቢሆን በመደጋገፉ የተጎዱትን እየነቀስን በማውጣት የቻልነውን መስራት የዜግነት ውዴታ ግዴታ ነው ባይ ነኝ  !

ሁሉም ለበጎ ነው  !

ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 5 ቀን 2007 ዓም

ኢትዮጵያ፡ “መፍትሔው ፍቺ ነው (ጌታቸው ኃይሌ)

$
0
0

Ethiopian Flagስለ ኢትዮጵያ ለማወቅ ፈልጎ መጻሕፍት የሚያገላብጥ ባይተዋር መጀመሪያ የሚታየው የሀገሪቷ ጥንታዊነትና ውበቷ፥ የነዋሪዎቿ መልከ መልካምነትና በብዙ ጎሳዎችና ነገዶች መኖሪያነቷ ሲሆን፥ እነዚህ መልካካም ኢትዮጵያውያን በፖለቲካው ረገድ ዕድለ ቢሶች መሆናቸው ነው። የፖለቲካ ለውጥ ለማምጣት፥ በተለይ በኛ ዘመን፥ ከፍ ያለ እንቅስቃሴ ተካሂዷል፤ ብዙ ሕይወትም አልፏል። ግን እንቅስቃሴውን መርተው መንግሥት ለመገልበጥ የቻሉ ሁሉ፥ “ካስወገድነው አገዛዝ የኛ አገዛዝ ይሻልሃል፤ እነ እገሌን አደኽይተን አነ እገሌን አናበለጽጋለን፤ በረዢም ዘመን ትግል ካስወገድነው እስር-ቤት መሰል አገዛዝ የኛ እስር-ቤት መሰል አገዛዝ ይሻላል” የሚሉ እንጂ ሕዝቡን ከአገዛዝ ነፃ የሚያወጡ አልሆኑም። እንዲያውም ያቋቋሙት አገዛዝ “ከድጡ ወደ ማጡ”” የሚባል አገዛዝ ነው። አይፈረድባቸውም፤ እነሱ የሚያውቁት ምን እንደሚፈልጉ እንጂ ሕዝቡ ምን እንደሚፈልጉ አያውቁም። ከየት አግኝተው ይወቁት? የሚያውቁት አያገባቸው ገብተው መፈትፈትና መጕረስ ነው። “ኢትዮጵያን ከአገዛዝ ነፃ አውጥቶ ዴሞክራሲን አጎናጸፋት” የሚል የታሪክ ክብር የሚቀዳጅ ጀግና ማን ይሆን? ለጊዜው የሚታየኝ እንከን የለሽ ንጹሕ ምርጫ የሚፈቅድ ባለሥልጣን ወይም የምርጫውን ሕግ የሚያስከብር የፖሊስ አዛዥ ነው። --[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]——-

ፌደራል ፖሊሶች ለሚፈጽሟቸው ግድያዎች ተጠያቂው ማን ነው? (ከዳዊት ሰለሞን)

$
0
0

dawit

ከዳዊት ሰለሞን

ይህ ጥያቄ በቀጥታ በመንግስት ትዕዛዝ የተፈጸሙ ግድያዎችን አይመለከትም፡፡እንደውም በፓርላማ ከቀረበው ረቂቅ አዋጅ አንዱ ‹‹በግዳጅ ላይ ያለ የመንግስት ታጣቂ ለሚፈጽመው ጥፋት ተጠያቂ እንዳይሆን ››የሚሞግት ነው፡፡
ፓርላማው 446 ለ 1 የሚመራ በመሆኑም ገዢው ፓርቲ የፈለገውን አዋጅ የማውጣት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡በዚህ ገጽ ግን ለማንሳት የወደድኩት ታጣቂዎች ከስራ ገበታቸው ውጪ እየፈጸሟቸው የሚገኙ ግድያዎች ሀላፊ ማን ይሆናል የሚለውን ነው፡፡
ንፋስ ስልክ አካባቢ የመንግስት የሰላም አስከባሪ አባል የነበረ አንድ መቶ አለቃ ጎረቤቶቹን በ35 የክላሽ ጥይት መግደሉና ህጻናቱን ያለ ወላጅ ማስቀረቱ አይዘነጋም፡፡
መቶ አለቃው ከታሰረ በኋላ በልዩ እንክብካቤ ተይዞ ወላጆቻቸውን ባጡ ህጻናት ላይ ይዘት እንደነበርና በኋላም አመለጠ ተባለ፡፡መቶ አለቃው መጨረሻ ላይ ስለመያዙ ተነገረ፡፡

ባህርዳር የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ አንዘነጋውም፡፡አፍቅሪያታለሁ ያለ ፌደራል ፖሊስ የ18 ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ ወንዝ ውስጥ ገብቶ ሞተ የሚል ወሬ ተናፈሰ፡፡

ቂርቆስ መንደር በምትገኝ የሴተኛ አዳሪዎች ሰፈር እንዲሁ የእኔ የሚላትን ሴተኛ አዳሪ ከሌላ ወንድ ጋር ተኝታ በማግኘቱ ፌደራሉ በሁለት ጥይት ደረቷን መትቶ ለህልፈት ዳረጋት ፣ከሴትየዋ ጋር የነበረው ጎልማሳም እግሩን በጥይት ለመቆረጥ በቅቷል፡፡
ይህ ፎቶ ግራፍም በተመሳሳይ መንገድ በፌደራል ፖሊስ ህይወቱን በግፍ ስለ ተነጠቀ ወጣት የሚጮህ ነው፡፡
ጅማን በእንባ፣በድንጋጤና በተቃውሞ የሞላ ክስተት የተስተናገደው በፌደራል ፖሊስ ነው፡፡በምሽት ሰው ቤት ሰብሮ የገባው ፖሊሱ አንዲት አይነ ስውር እናትና ልጃቸውን ቀጥፏል፡፡

ግለሰቡ ስለ መያዙም ተነግሯል፡፡ግን ይህ ነገር በገዳዮቹ መያዝ ብቻ የሚያበቃ መሆን የለበትም፡፡ተጠያቂነቱ ወደ ላይም መውጣት አለበት፡፡መሳሪያ መያዝ የማይገባቸው፣ሰብዓዊነት ምን ማለት እንደሆነ የማይረዱ፣ግደሉ ሲባሉ ከመግደል የማያመነቱ፣መሳሪያ ሲጨብጡ ጭንቅላታቸውን ቃታው ጋር የሚያደርጉ ሰዎችን መለዮ እያለበሱ ስልጣናቸውን ለማራዘም እስከጠቀሟቸው ድረስ ስለሚፈጽሙት ዘግናኝ ድርጊት ደንታ የሌላቸው አካላትም መጠየቅ ግድ ይላቸዋል፡፡

የሟቾቹ ደምም በተኳሾቹ ላይ ብቻ ሳይሆን ነፍጥ ባሸከሟቸው ሀይሎች ላይም ይጮሃል፡፡

የማለዳ ወግ …እኔ ፣ እነሱ እና “ቁንጽል ”የሚሉት መረጃ … (ነቢዩ ሲራክ)

$
0
0

የማለዳ ወግ …
እኔ ፣ እነሱ እና “ቁንጽል ” የሚሉት መረጃ …
* ደረቁ የካልድ እንባ
*  ” ለዚህማ ነፍስህንስ ብትሰጥ ምን አለበት! ” እናቴ …

Nebiyu Sirak ሳውዲ ውስጥ በገፋሁት ሁለት አስርት አመታት ከተለያዩ ወገኖቸ ከውስጥም ከውጭም ስደተኛውን በሚመለከት ተጨባጭ መረጃዎች ይደርሱኛል። የሚያመውን ምስል የያዙ መረጃዎችን ከሙያ አንጻር ብቻ ሳይሆን መረጃውን የሚመለከቱትን ወገኖቸን ስሜት እንዳልጎዳ በሚል በጽሁፍ ከመግለጽ ውጭ አልለጥፋቸውም ። መረጃዎችን ይዠ በቅርቤ ወዳለው የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ቀርቤ አሳይቻቸውም አውቃለሁ ። በመብት ጥበቃ አልተጋችሁምና ትጉ ስላቸው ምክሬን አይቀበሉትም።  ይባስ ብለው በአይነ ቁራኛ ያዩኛል ፣ ካንድም ሁለት ሶስቴ ከቆንስሉ ግቢ እንዳትደርስ ተብየም አውቃለሁ !  ነጻ ከሚባለው ኮሚኒቲ ድረስ ዘልቀው የአባልነት መታወቂያየ እንዳይታደስ አድርገው ያውቃሉ ! ” ሃገር ቤት አይገባትም ” የሚባለው ተራና የወረደ ማስፈራሪያ የተለመደ ቢሆንም ሃገር ቤት ስገባ ግን ችግር ገጥሞኝ አያውቅም … ቂም ተቋጥሮብኛልና ዛሬ በተፈታ ድራማ የመንግስ ተወካዮች ለሁለት ወራት ከከባድ ወንጀለኞች ማጎሪያ ወህኒ ስወረወር እንደ ዜጋ መብቴን ለማስከበር ቀርቶ ” የት ነው? “ብለው አልጡቁኝም  … ! ልብ በሉ የማወራው ላይ ላዩን ነው!

ያን ሰሞን በጠራራ ጸሃይ ሜዳ ላይ የወደቀች እህት ወደ መጠለያ አስገቧት ለማለት ወደ ተጠባባቂው የጅዳ ቆንስል ጀኔራል አቶ ሸሪፍ ከይሩ ቢሮ ጎራ ብየ መረጃ ሳቀብላቸው አጠር ያለች ውይይት አድርገን ነበር ፣ ብዙ ከተወያየን በኋላ በተደጋጋሚ ስደውልላቸው ለምን ስልኬን እንደማያነሱ ጠይቄያቸው ” ሁሉን የምታውቅ ይመስልሃል ፣ ግን አታውቅም…ቁንጽል መረጃ ይዘህ ፣ ጉዳዩን ፖለቲሳይዝ እንደምታደርግ ስለምናውቅ አንተባበርህም! ” ሲሉ እንቅጩን ነግረውኝ አዝኛለሁ !  በዋናነት ለዜጎች መብት ማከበር የመንግስቱ ከፍተኛ ሃላፊነትን ተሸክመው ከተቀመጡት ሃላፊ መስማቴን ይህች ሃገር የማናት ? አላልኩም ፣ ሃገሩም ህዝቡም የእኔ መሆኑን ጠንቅቄ አውቃለሁ !   ያም ሆኖ አሁን አሁን ሃገሯ የእኔም ጭምር ሆና የምወዳቸውን ልጆቸን ይዠ እንደ ኩሩ ዜጋ እረፍቴን በሃገሬ ለማድረግ አልታደልኩም! ” የምሰማው ጥሩ አይደለም ፣ ከመጣህ እረግምሃለሁ ፣ ለልጆችህ ኑርላቸው !” የምትለኝ መነኩሴ እናቴ ቃልና ምክሯን ለማክበር ግድ ብሎኝ ሃገር ቤት መሄዱን ሳልወድ በግድ ደጋግሜ ሰርዥዋለሁ! ቀዳሚውን ፈጣሪ ቢያውቀውም ለመሰረዝ ውሳኔ ያደረሰኝ የምሰማውን ማድፈራሪያ ግፊቱን ፈርቸ ሳይሆን  የምወዳት እናቴ በመጨረሻዋ የህይዎት ዘመኗ ላሳዝናት ስለማልሻ እንጅ ” የቆስል ስራውን በማደናቀፍ! ” አለያም “ሽብርተኛ ደጋፊ “የሚል ክስ ተለጥፎብኝ  መታሰር መገረፉን የሚፈራ ልብ ኑሮኝ አይደለም  !  በማምንበት የአረብ ሃገር ስደተኛ ዜጎች መብት ይከበር ተዛማጅ መረጃና ሂስ በመሰንዘሬ  የሚመጣውን ለመቀበል ነፍሴ በጸጋ ልትቀበል ከቆረጠች አመታት አልፈዋል …

ይህን ሁሉ ማለቴ ያለ ነገር አይደለም ፣ ምሽት ላይ ሁለት ተቃራኒ ክስተትን አስተናግጃለሁና ነው ። አንዱ የቤሩቷን ብርቱላንና በኦማን የአልማዝን አበሳ ባቀረብኩበትየመረጃ ግብአቴ የተበሳጨ ወንድም ” … ደላላ ፣ ቆንስል ፣ መንግስት ምንቴስ እያልክ ፣ ቁንጽል መረጃ ይዘህ መንግስትን ታጋልጣለህ ፣ ገጽታ ታበላሻለህ ” የሚል ሰብዕናን መሰረት አድርጎ መወያየት የማይሻ ፣ ሲያስረዱት የማይገባው ጨካኝ  አጋጥሞኝ ነው …ሌላው ክስተት ደግሞ የዚህ ተቃራኒ መረጃ ሲሆን ” የሳውዲውን ትተህ ለምን ወደ ኦማንና ሊባኖስ ትሔዳለህ ?” ያለኝን አድራሻው የጠፋብኝን ወንድም አግኝቸው ፣ ከዚህ ቀደም የማወረቀውን መረጃ ልኮልኝ በአሳዛኙ ታሪክ ተረባብሻለሁ ! የሃገሬን ገጽታ እንደማላከፋ ፣  ቁንጽል መረጃ እንደማላውቅ ለዛሬው ሞጋቸና ለቆንስል ሸሪፍ ከይሩ ለትናንት ምሽቱ ሞጋቸ ምላሽ ይሆነኝ ዘንድ ሁለተኛውን ክስተት “ጉዳይ  እንዲህ ነው ” ብየ ልጀምረውና በቀጣይ ቀን ዝርዝር መረጃውን ላሳያችሁ ቆርጫለሁ  ! ጀሮ ያለው ይስማ  !

ወጣቱ ካልድ በከዛን ሆስፒታል …
ነገሩ እንዲህ ነው ፣ በሁለት አመት በፊት ገደማ በቀረበ የመረጃ ቅበላየ ” አንዲት እህትና አንድ ወንድም በየመን ሳውዲ የጠረፍ ከተሞች የመኪና አደጋ ደርሶባቸዋል ፣ ከተቻለ በፍርድ ቤት የኢንሹራንሱን ጉዳይ ተከታትላችሁ ጨርሱ ፣ አለያም ወደ ሃገር የሚገቡበትን መንገድ ፍጠሩ! ” ብየ ከሰላ ሂስ ጋር ጽፊ ነበር ። … ያን ጽሁፍ ካቀረብኩ በኋላ አልፎ አልፎ ስለጉዳዩ መረጃ የሚያቀብለኝ ወዳጀ ተጎጅዎች ወደ ሃገር በመላኩ ረገድ የጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ምንም የሰራው ስራ አለመኖሩን አጫወተኝ ፣ ምንም ማድረግ ስለማይቻለኝ እኔና እርሱ የሚቻለንን ማድረጋችን ከህሊና ጸጸት ድነናል በሚል ብቻ አስረዳሁት ። ከዚያ በኋላ በግል ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ዘንድ በአካል ሳይቀር ቀርቤ ለማስረዳት ሞከሬ  ” ጉዳዩ በፍርድ ቤት ተይዟል።፣ እኛ ምንም ማድረግ አንችልም  ” ማለታቸውን አስታውሳለሁ  ! ይህ ከሆነ ታዲታ ቆይቷል …

የጀዛኑ ወዳጀ አድራሻ በመቀየሩ ስለ ወጣት ካልድ የማገኘው መረጃ ተቋረጠ ። ያም ሆኖ ከስድስት ወር በፊት አንደ ሌላ ወንደም ካልድ እስካሁም በሆስፒታል የመኖሩን ፣ ሴቷ እህት ግን ከወራት በፊት ወደ ሃገር ቤት በአሳር በመከራ መግባቷን የጻፍኩትን የተከታተለ የጀዛን ነዋሪ በህዝብ ስልክ ደውሎ ” ማንነቴን አልነግርህም ፣ ካልድ በስቃይ ላይ ነው ፣ ወይ ሃገር ቤት አልገባ ወይ … ” እንዳለ ንግግሩን ሳይቀጥል የሳግ ድምጽ ተከትሎ ስልኩ ተዘጋ  ! ከቦታው የደረሰኝ የዚህ ሌላ መረጃ ባለቤት ስሜት መጎዳቱ ገብቶኛልና ውስጤን አወከው …ደነገጥኩ  ! ያ ሰው ግን ከዚያ ወዲህ ደውሎልኝ አያውቅም ፣ ከዚያ ጊዜ በኋላ በኩባንያ ስራ ምክንያት በተደጋጋሚ ወደ ጀዛን ብሔድም ከስራ ጫና የተነሳ ወደ  ሆስፒታሉ መሄድ ገደደኝ …እናም በቃ የሚወተውት የሚያስታውሰኝ ወዳጀ ርቋልና ካልድን ረሳሁት …

ዛሬ እኩለ ሌሊት ካልድን በሚመለከት አንድ አስገራሚ መረጃ ደረሰኝ ፣ ያ ወዳጀ በኦማን ለአካል ጉዳት ተዳርጋ ሀገር ቤት ለገባችወደ ለአልማዝ እርዳታ ከተሰራጨ የስልክ ቁጥሬን አግኝቶ መደወሉን አጫወተኝና ወደ ጉዳያችን ማወረጋት ጀመርን … ካልድ ስላለበት ሁኔታ ይነግረኝ ገባ ፣ አላመንኩም ፣ ለክፉ ለደጉ በሚል መረጃ አፍቃሬ መሆኔን ያውቃልና ” ተመልከተው!” ብሎ ካልድ ያለበትን ሁኔታ የሚያሳየውን መረጃ ላከልኝ … ተደመምኩ ፣!  የደረሰኝ መረጃ ለ”ቁንጽል መረጃው ” ውንጀላቸው ምላሽ ከመሆን ባለፈ መንግስት በዜጎቹ መብት ጥበቃ ዙሪያ ስለማይተጉ ሃላፊዎችና ጽንፈኛ ደጋፊዎቹ የተንሸዋረረ መረጃ ትቶ እውነቱን ይረዳ ዘንድ ይህ መረጃ ማሳያ ከሆነው ላቀርበው ወደድኩ ! መንግስት እንደ ቀደመው  ማየት ፣ መስማት ካልቻለ ደግሞ እየሆነ ያለውን እስኪያይ፣ እስኪሰማና  እስኪገባው የሚያገባን እንጮሃለን  !  በቃ ! ይህን ነው የምለው  ! …

ምናልባት እናቴ የወጣት ካልድን አሳዛኝ ታሪክ ከተንቀቀሳቃሽ ምስሉ ጋር እያሳየሁ ባጫውታት አሁን አሁን የሚነገራትን እየሰማች  ” ወደ ሃገር አትምጣ ፣ ጊዜው ለልጆችህ ስትል ኑርላቸው !” ! የምትለኝን አትደግምልኝም!  ሰብእናን እንዳስቀድም ኮትኩታ ያሳደገችኝ የእናት ስስት ምክሯን ትታ   ” ለዚህማ ነፍስህንስ ብትሰጥ ምን አለበት!  ” ብላ ተዘጋጅቶም ከሆነ ወደ ገሃነምም ቢሆን መርቃ እንደምትሸኘኝ ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ  …

አዎ  ! የወጣቱን ታሪክ በግርድፍ ከደረሰኝ የወዳጀ መረጃ ተንተርሸ በቀጣይ የማለዳ ወጌ የምናወራው ይሆናል …
Dry tears of Khalid Nebiyu Sirak: http://youtu.be/H5N4KyeWPNo
እስኪ በቃችሁ ይበለን  !

ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 6 ቀን 2007 ዓም


በኢትዮጵያችን በጥርስና በጥፍር የሚደረግ ትግል እንዴት ይቁም? (ግርማ ሠይፉ ማሩ)

$
0
0

ግርማ ሠይፉ ማሩ

girmaseifu32@yahoo.com

girmaseifu.blogspots.com

(ግርማ ሰይፉ)

(ግርማ ሰይፉ)

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ/አንድነት አሳዛኙን የ2002 ምርጫ ውጤት ተከትሎ ፍራሽ አንጥፎ ኢህአዴግን ምርጫ ዘረፈ ከሚል መደበኛ ለቅሶ መውጣት አለብኝ ብሎ ቁርጠኛ ውሳኔ በመወሰን ውስጣችንን መፈተሸ ተገቢ አቅጣጫ ነው ብሎ በማመን በእኛ በኩልስ የነበረው ችግር ምንድነው? የሚለውን ጥያቄ አንስቶ ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት አድርጎዋል፡፡ ይህ ነገሮች ወደ ውጭ ከማላከክ በዘለለ ሙሉ ቁጥጥር ባለን በራሳቸን ላይ የውስጥ ፍተሻ ማድረግ ጠቃሚና ተገቢ ነው ከሚል እምነት የመነጨ ነበር፡፡ ይህ ማለት ግን የውጭ ጫናዎች በተለይም የኢህአዴግ አፈና የነበራቸውን ተፅዕኖ አሳንሶ ማየት እና የኢህዴግን አፋኝነትን ዝቅ አድርጎ መመልከት አድርገው የሚውስዱ ሰዎች አይጠፉም፡፡ ዋናው ጉዳይ እና ቅድሚያ መሰጠት ያለበት የውሰጥ ጥንካሬና ድክመትን ማወቁ ነው የሚለው ነበር፡፡ በዚህም መነሻ አንድነት በተቃዋሚ ፓርቲዎች ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን የአምስት ዓመት ሰትራቴጂና ዕቅድ አዘጋጅቶ ለህዝብ ይፋ አድርጓል፡፡ ይህም ሆኖ ግን ሪፖርተርን የመሰሉ ጋዜጦች ተቃዋሚዎችን በጅምላ የሚመሩበት አቅጣጫ የሌላቸው አድርገው መፈረጃቸወን አላቆሙም፡፡ ሌሎችም ቢሆኑ ይህን ተከትለው ከማሰተጋባትና ተቃዋሚዎችን በጅምላ ከመክሰስ ወደኋላ አላሉም፡፡ ለማነኛውም ፍረጃው እንደተጠበቀ ሆኖ አንድነት ያለፉትን አራት ዓመታት ጎዞዉን ባስቀመጠው ሰትራቴጅና አምስት ዓመት ዕቅድ መሰረት አድርጎ ቀጥሏል፡፡ የእቅዱ ማጠቃለያ ዘመንም ከምርጫ ሁለት ሺ ሰባት ምርጫ ጋር የሚገጣጠም ነው፡፡

ይህ የአምስት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ወደፊት እንደሚካሄድ ታሳቢ ተደርጎ የመጨረሻው ዓመት ሊኖረን የሚገባው ዋነኛ ሰራ ምርጫን መሰረት ያደረገ እንደሚሆን ይታወቃል፡፡ ከዚህ አንፃር ገዢው ፓርቲ በጥርሱም በጥፍሩም ምርጫን ለማሸነፍ እየተንቀሳቀሰ ሲሆን እግረ መንገዱን ደግሞ የተቃዋሚዎችን በተለይም ደግም የአንድነትን ጥርስ ማውለቅና ጥፍር ማዶልደሙን ተያይዞታል፡፡ የጫወታው ህግ በጥርስም በጥፍርም መጫወት የሚፈቅድ ከሆነ ተወዳደሪዎች በተመጣጣኝ ጥርስም ጥፍርም ሊኖራቸው ይገባል፡፡ በቦክስ ጫወታ ደረጃ የሚወጣው በኪሎ ነው፡፡  አጫዋቹም/ዳኛውም ጫወታው ከመጀመሩ በፊት ቅድሚያ ሰጥቶ ማረጋገጥ ያለበት ይህን ጉዳይ ሁሉም ተወዳዳሪዎች ማሟላታቸውን ነው፡፡

 

አንድነት በዚህ ዓይነት የጥርስና የጥፍር ጫወታ ውስጥ ገዢው ፓርቲ ለማድረግ እንደሚፈልገው የተወዳደሪን ጥርስ ማርገፍና ጥፍር ማዶልዶም ተመጣጣኝ ምላሹ የገዢውን ፓርቲ ኢህአዴግ ጥርስ ማርገፍና ጥፍር ማዶልዶም መፍትሔ ይሆናል ብሎ አያምንም፡፡ ለውድድሩ ጥርስም ጥፍርም አስፈላጊ ከሆነ የአንድነት ፓርቲ ጥርስና ጥፍር እንዳይጎዳ መጠበቅ ቅድሚያ ይሰጠው ነው፡፡ ይህ ነው በቁጥጥራችን ስር የሚገኘው እና ዋና ትኩረታችን ሊወስድ የሚገባ እንዲሁም ተገቢ ጊዜ መስጠት አለብን የምንለው፡፡ የገዢውን ፓርቲ ጥርስ ለማርገፍና ጥፍርሩን ለማዶልዶም የምናባክነው ጊዜ የራሳችን በመጠበቅ ብሎም በቁርጠኝነት ባለማስደፈር ቢሆን የበለጠ አዋጭ ነው ብለን እናምናለን፡፡

በገዢው ፓርቲ መንገድ የምንሄድ ከሆነ ግን ወደፊት ለሚደረግ ውድድር በሁለቱም ወገን የሚኖሩ ተወዳደሪዎች በድድ እና በዱልዱም ጥፍር የሚወዳደሩ ይሆናሉ ማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ የጫወታውን ህግ መለወጥ የሚጠይቅ ይሆናል፡፡ በዛሬው የጥርስና ጥፍር ተምሳሌት ዋነኛ ወካይ ባህሪዎች በሁለቱም ጎራ የተሰለፉ ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን ነው፡፡ ኢህአዴግ የተቃዋሚዎችን በተለይ የአንድነትን ጥርስና ጥፍር ላይ አደጋ አደረሰ ማለት በየደረጃው ያሉ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች ላይ የሚወስዳቸው ቅጥ ያጡ ህገወጥ እርምጃዎች ማለታቸን ነው፡፡ በአፀፋው አንድነት ይህን ያድርግ ሲባል ደግሞ በኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች ላይ ቅጥ ያጡ ሕገ ወጥ እርምጃዎች እንውሰድ ማለት ነው፡፡ የእነዚህ ድምር ውጤት ኢትዮጵያዊያንን በፖለቲካ አቋማቸው ከመጉዳት የሚተናነስ አይደለም፡፡ በዚህ ሁኔታ በተጎዳ ህዝብ ውስጥ ወደፊትም ቢሆን የተሸለ እና የሰለጠነ አማራጭ ይዞ በፖለቲካ መወዳደር ይቻላል የሚል እምነት አይኖርም፡፡ ለዚህም ነው ጉልበታችንን የኢህአዴግ አባላትን ለመጉዳት ወይም ለመበቀል ሳይሆን የአንድነት አባላትና ደጋፊዎችን አቅም በማሳደግ የአይደፈሬነት ሰነልቦና ማዳበር መሆን ይኖርበታል የምንለው፡፡

በአንድነት በኩል የአባላቶቻችንን አቅም እናሳድጋለን ብለን ስንነሳ በዋነኝነት በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሚደረግ ውድድር የሚመነጨው አንዱ ሀገር ወዳድ ሌላው ጠላት ነው ከሚል መንፈስ፣ ወይም በግል በደረሰብን በደል በቁጭትና ለበቀል መሆን እንደሌለበት በማሰተማር ነው፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚለያዩት በሚመርጡት የርዕዮተ ዓለም፣ ይህን ለመተግበር በሚያወጡት ፖሊሲና የማስፈፀሚያ ስትራቴጂዎች መሆኑን በማስረዳት በማስከተለም እነዚህ ልዩነቶች ሀገርን ሊጎዱ እንደሚችሉ ለህዝብ በማሰየት ህዝብ ለሚሰጠው ብይን ተገዢ ለመሆን ዝግጁ ሲኮን ነው፡፡ ይህን ልዩነታችንን ከጠባብ ቡድናዊ/የፓርቲ ወይም ሌላ ስብስብ ፍላጎት ከመነሳት “ሀገር ወዳድ እና የሀገር ጠላት” በሚል እንድንፈራረጅ ምክንያት ከሆነ የጋራ ሀገር እንዲኖረን እየሰራን ነው ማለት አይቻልም፡፡ ኢትዮጵያ ሀገራችን ለሁሉም ፓርቲዎች የጋራ መኖሪያ ከመሆን በዘለለ የሁሉም ፓርቲዎች አባላት የሚኖሩባት ብቻ ሳትሆን ለልጅ ልጆች በተሻለ ደረጃ ልናስተላልፋት ትልቅ ራዕይ ሰንቀን የምንቀሳቀስ መሆኑ በሁሉም ዘንድ መታወቅ አለበት፡፡ ኢትዮጵያችን እንድትኖር እኛም በእርሷ እንድንኮራ በሁሉም ጎራ የተሰለፍን ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ከፍተኛ ሀገራዊ ኃላፊነት እንዳለብን አውቀን መንቀሳቀስ ይኖርብናል፡፡

በኢህአዴግ በኩል የሚገኙ አባላት ብሎም ከፍተኛ አመራሮች ጭምር የተቃዋሚ ፓርቲዎችን “ኪራይ ሰብሳቢ” ከሚል ቅጥ አንባሩ ከጠፋው ፍረጃ በላይ ግልፅ ሆኖ በወጣ መልኩ በተቃዋሚ ጎራ የተሰለፍን ዜጎች በፍፁም ለሀገር ደንታ የሌለን አድርገው መሳል የተለመደና አስልቺ ፕሮፓጋንዳ ከሆነ ቆይቶዋል፡፡ ይህ በእውነቱ የኢህአዴግ በጥርስም በጥፍርም ለመጫወታ እንዲመቸው የሌላውን ጥርስ ማርገፍና ጥፍር ማዶልዶሚያ ስትራቴጂው ነው፡፡ ይህ መንገድ ግን ብዙ ርቀት የማያስኬድ ብቻ ሳይሆን ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም የሚበጅ ነው የሚል እምነት የለንም፡፡

በተቃዋሚ መስመር የተሰለፍን ሰዎች መካከልም ኢህአዴግን መሳደብ እንደ ዋና የትግል ሰልት የተያዘ እስኪመስ ድረስ ጥግ እንደምንሄድ አምኖ መቀበል ስህተታችንን ለማረም ጉልዕ ድርሻ አለው፡፡ አንዳንዴም የሃሳብ ልዩነትን በሰለጠነ መንገድ ከመግለፅ ይልቅ ሰነምግባር በጎደለው ሁኔታ በተለይ የግለሰቦችን ስብዕና የሚነኩ አላስፈላጊ የቃላት ጫወታዎች እንዳሉ እንረዳለን፡፡ “ቅኔው ሲጣፋበት ቀረርቶ ሞላበት” የሚለው አባባል በሁለቱም ጎራ የመከራከሪያ ሃሰብ ድርቀት ምልክት ሊሆን ይቻላል፡፡ ይህንን ከመሰረቱ ለመቅረፍ ከላይ እንደተገለፀው አባላትን በስነምግባር መኮትኮት እና ዋነኛው የፓርቲዎች ልዩነት መሰረት መሆን የሚገባው የፖሊሲና የስትራቴጂ ጉዳዮች ላይ እንዲያተኩሩ ማድረግ ነው፡፡ ይህ ሲሆን በከፍተኛ ሀገራዊ መግባባት ሰሜት መንቀሳቀስ ይቻላል የሚል ፅኑ እምነት ይዳብራል፡፡

 

“አንድነት የአዲሱ ትውልድ ፓርቲ ሆኗል” (አቶ አስራት አብርሃም)

$
0
0
Asrat-Abereha2

አቶ አስራት አብርሃም

አቶ አስራት አብርሃም በእስር ላይ የሚገኘው የአቶ ሃብታሙ አያሌው የስራ ኃላፊነት ተክቶ የአንድነት ፓርቲ ተጠባባቂ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሆኖ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ ስለ ፓርቲው ወቅታዊ ሁኔታና የወደፊት አቅጣጫ በተመለከተ ከአቶ አስራት ጋር ተወያይተናል፡፡ ፍቱን፡-በዚህ ወቅት መንግሥት በያዘው አቋም እና ተቃዋሚዎች ባላቸው ደካማ አደረጃጀት እና ምላሽ ምክንያት ፓርቲዎቹ እንኳን የህዝቡን መብት ከጥቃት ሊከላከሉ ለራሣቸው መሆን አቅቷቸዋል፣ የፓርቲዎች መኖር ጉዳት እንጂ ጥቅሙ አልገባንም የሚሉ ድምጾች በዝተዋል?

አስራት፡-ባለው ነባራዊ ሁኔታ ነው የሚወስነው ፣ በእርግጥ እዚህ አገር ችግር አለ:: ተቃዋሚዎች በውጪያዊ ተጽዕኖና በውስጣዊ ችግር እንደተፈለገው ተጠናክረው ሊወጡ አልቻሉም:: እየተከፋፈሉ፣ እየፈረሱ፣ እየተገነቡ ነው ያሉት:: በዚህ ምክንያት የአቅመቢስ ሆነዋል:: ይህ ሂደት መቀየር አለበት ብለን ነው የምናስበው:: ከዚህ ጋር ተያይዞ በአንድነት ውስጥ ፖለቲካውን በተሻለ አቅምና ራዕይ መምራት ያስፈልጋል፣ አዲስ አመራር መምጣት አለበት የሚል አቋም አምጥተዋል:: ያንን የለውጥ ፍላጐት ተከትሎ ፕሬዝዳንቱ ስልጣናቸውን ለቀው ለውጡ መጥቷል:: በዚህም ምክንያት ፓርቲውን ለሚያጠናክር አንዳንድ ሥራዎች እየሠራን ነው:: ፓርቲው የህዝብ ፓርቲ የሚሆንበትን መንገድ እየፈለግን ነው:

:በእርግጥም ፓርቲዎች ካልተጠናከሩ በስተቀር ብቅ የሚሉትን የፖለቲካ አመራሮች ለእስር እየዳረጉ፣ ፓርቲ እየተጐዳ፣ የህዝብ ሞራል እየተዳከመ የሚሄድበት ሁኔታ ሊቀጥል ይችላል::

[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

አማራ፣ ኦሮሞ፣ ስብአዊ መብቶችና ድርጅቶቻቸው፣ ተጠንቀቅ አማራ! ከቦጋለ ካሳዬ

$
0
0

አማራ፣ ኦሮሞ፣ ስብአዊ መብቶችና ድርጅቶቻቸው

amaraየደላቸው… የሰው ልጅ ይቅር፤ ማንኛውም ህመም ሊሰማው የሚችል ፍጡር አይጠቃ! አይገደል! ብለው እሪ! እሪ! ይላሉ። ያነባሉ። እንቅልፍ አይወስዳቸውም። የሌሎች ስቃዮች እነርሱንም ያስቃያቸዋል።
አንዴ ተማሪ እያለን የደብረ-ብርሃንን የብርድ ልብስ ፋብሪካ ልንጎበኝ ሄድን። አስተማሪያችን ፕሮፌሰር ፓንዲታ የሚባል ህንድ ነበር። ለምሳችን ስጋ ያለበት ሳንዱውች ተዘጋጅቶአል። የደብረብርሃን ብርድ ለጠኔ ዳርጎን ነበርና ሰፍ ብለን ሳንዱቻችንን መግመጥ ጀመርን። አስተማሪያችን ግን ከንፈሩ ደርቆ አይን አይናችንን ያየናል። ለመብላት ፈልጎአል። “ለምን አትበላም?” ብለን ብንጠይቀው፤ “ስጋ አልበላም። እምነቴ ማንኛውንም ፍጡር አትግደል ይላል።” ብሎን እርፍ!
በሆላንድ የእንሳስት መብት ተሙዋጋች የፖለቲካ ፓርቲ አለ። አሁን ዳች ፓርላማ ውስጥ ሁለት መቀመጫ አለው። ፓርቲው መሬት ማንኛውንም የሰው ልጆች ፍላጎቶች ለማሙዋላት ትችላለች። ይሁን እንጂ የሰዎች ስግብግብነትን ለማሙዋላት አትችልም ብሎ ያምናል። እንደ ፓርቲው ከሆነ ለምሳሌ የእንስሳትና እንስሳት ተዋጽኦ እንዱስትሪ፤ 30% በተፈጥሮ ይገኙ የነበሩ የእንሥሣትና የእጽዋት ዘሮችን በማጥፋት ተጠያቂ ነው። ከብቶችንም ለማደለብም ሆነ የወተት ጎርፍ ለማምረት መኖ በገፍ ስለሚያስፈልገው፤ በዚህም ሳቢያ መሬት ከድሃ ገበሬዎች ስለሚቀማ፤ የአለም ርሃብ እየተባባሰ የመጣበት አንዱ ዋናው ምክንያት ከእንስሳትና እንስሳ ተዋጾእኦ እንዱስትሪ ተግባር ጋር የተያያዘ መሆኑን ያረጋግጣል። በተጨማሪም የእርድ እንሳሳት ሲታረዱ ህመም እንዳይሰማቸው ይደረግ ይላል። አንዳንድ እንስሳት በተለይ አሳማዎች ለእርድ ሲቀርቡ ያለቅሳሉ! አንጀት ይበላል ነገሩ።
አሜሪካውያት ሴቶች የምጥን ህመም ስለሚፈሩ ማደንዘዣ ይወጋሉ ይባላል። በአውሮፓ ግን ሴቶቹ ማማጡ በተፈጥሮ ያለ ነገር ስለሆነ፤ እናምጣለን! የምን ማደንዘዣ ነው… እቴ! ብለው የምጡን ህመም ጥርሳቸውን ነክሰው ይጋፈጡታል።
የሰው ልጅ የቆየ እምነትም ይሁን ዛሬ በሰለጠነው አለም እንደምናየው እንስሳትም ይሁን ሰዎች እንዳይሰቃዩ የሚደረጉትን ጥረቶች ጨረፍ ካደረግን ወደ ዋናው ጉዳያችን እንግባ።
በኢትዮጵያ መገዳደል አዲስ ነገር አይደለም። በታሪካችን ግዛት በማስፋፋት፣ የተለያዩ ጭቆናዎችን በመቃወም፣ በሃይማኖት ሳቢያ የደረሱ እልቂቶች አሉ። ቀይና ነጭ ሽብር ትልቅ ጠባሳ የጣሉቡን እልቂቶች ናቸው።
አይኖችቻን ይጥፉ! እምቢ አናይም ካላልን፤ በህወሃት አገዛዝ በአማራ ላይ አላባራ ያለው ግድያ ግን ለየት ያለ ነው።
1. በኢትዮጵያ የአማራ(ሸዋ) ገዢ መደብ እየተባለ የሚጠራውን(ክላፋም እንደጻፈው፤ 48% ኦሮሞ ነው፣32% አማራ፣ትግሬዎችና ሌሎች ናቸው) እንደጠላት መፈረጅ የጀመሩት የብሄር-ብሄረሰብ ጥያቄ ያነሱ ሰዎችና ድርጅቶች ናቸው። በወገኖቻችን በኩል የጉዳዩ አነሳስ ለእኩልነት ተብሎ የታሰበና አማራን ለጥቃት ኢላማ ለመዳረግ ሆን ተብሎ የተደረገ አልነበረም ብሎ ማሰብ ይቻላል። በተጨማሪም በአገራችን የመናገር፣ የመጻፉና የመወያየት ነጻነት ስለሌለ እንደዚህ ያለው ፖለቲካ ወደሁዋላ ይዞ የሚመጣውን መዘዝ አስቀድሞ ማየት ዛሬ ላይ ተቀምጦ ያለፈውን እንደመተቸት ቀላል ነገር እንዳልሆነ እንገነዘባለን።
1.2 ይሁን እንጂ ዶ/ር መራር ጉዲናም እንደታዘበው፤ በተለይ ለእኩልነት አማሮች ከማንኛው የበለጠ ትልቅ ዋጋ ቢከፍሉም ዛሬ ግን ተክድዋል። በሁሉም በሚለው ነገር መስማማት ባይቻልም መራራ ህሊና ያለው ሰው ነው። እንደ አፈንዲ ሙተኪ አግላይ፣ ስድና እሥስት አይደለም።
2. እ.አ.አ በ1995 ዴፕሎማሲ በሚል ሄንሬ ኬሲንጀር በጻፉት መጽሃፍ ውስጥ ፤ አሜሪካ የአንደኛው ዓለም ጦርነት እንዳለቀ(1919) ፤ ዳግም በአውሮፓ ጦርነት እንዳይነሳ አውሮፓውያንን አንዱ አገር አንዱን እጠቀልላለሁ በሚል የሚደረግ የሃይል ግንባታ ፍክክር እንዲያቆሙና፤ ከእንግዲህ ብሄሮች የራሳቸውን እድል በራሳቸው መወሰን አለባቸው የሚለውን መርህ እንዲከተሉ ማስጠንቀቁዋን እናነባለን። ይህ የአሜሪካ አለምን በብሄር የማደራጀቱ ፓሊሲ በክሊንተን አስተዳደርም ዮግዝላቪያን በማፍረስ በጉልህ መከሰቱን አይተናል። በኢትዮጵያም ጊዜውን ጠብቆ ይቀር ይሆን?
3. የተቀረው የአፍሪካም ፍዳ ይኼው ነው። ምንም እንኩዋን አህጉሩ (ከኢትዮጵያ በስተቀር) በአውሮፓውያን ተቀራጭቶ የዛሬዎቹ አገሮች ቢፈጠሩም፤ ሰላም እንዲሰፍን በሚል ሽፋን የአፍሪካን ሃብት ለማራቆት በጎሳ ላይ የተመሰረቱ አገሮች እንዲመሰርቱ የሚያቀነቅኑ አሉ። አንዱ አቀንቃኝ የመለስ ዜናዊ አማካሪ የነበረ “ተራማጅ” የሚባል ሶሻል ዴሞክራት ነው። ቻይና ሳይታሰብ መጣና ጫወታውን ለውጠው እንጂ።
4. ወደ ኢትዮጵያ ስንመለስ፤ ጨቁዋኙ አማራ፤ ተጨቁዋኝ ሊሎቹ ተብሎ ህወሃትን፣ ኦነግንና ኦብነግን በሚደግፉ የውጭ ኃይሎች ሆን ተብሎ ድርሰት ተደርሶአል። በጉዳይ ላይ ብዙ መጻህፍት ተጽፈዋል። ብዙ ፒ.ኢች.ዲዎች ተመርቀውበታል። ይህቺን ማስታወሻ ዛሬ ቅዳሜ በምጽፍበት ሰዓት እንኩዋን የኢትዮጵያ ማህበር በሆላንድ ሁለት በዚሁ ድርሰት ዶ/ር የተባሉ ቀንደኛ የአማራ ጠላቶች ጠርቶ ስለ ኢትዮጵያ የወደፊት ፖለቲካ አቅጣጫ እንድንወያይ ጋብዞናል። እኔ ጠላቶቼን ቀደም ብዬ ስላማውቃቸው ከእነርሱ ጋር ስለ አገሬ አቅጣጫ መፍትሄ ለመፈለግ አልሂድም። የውይይት መብታቸውን ግን አከብራለሁ።
5. የውጭ ኃይሎች እነዚህ ብሄረተኛ ድርጅቶችን የሚደግፉበት ምክንያት ምንድን ነው? ህወሃትን የሚደግፉበት ምክንያቶች ግልጽ ናቸው። መሬት አግኝተዋል። ሽብርን ለመዋጋት በሚል ሰበብ ለሞት የሚማገድ የሰው ሃይል በቀላሉ ያገኛሉ። የህወሃት የጎሳ ፖለቲካም የኢትዮጵያን አገራዊ ስሜት ለማደብዘዝ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ከመሬቱም፣ከወታደር መማገዱም ሆነ እርስ በእርስ ከማናከሱ ፖለቲካ ህወሃት ተጠቃሚ ነው። ፕሮፌሰር ዓለማየሁ በሚገባ እንዳስቀመጡት፤ ህወሃት በምጽዋት የሚኖር የለማኞች አገዛዝ ነው።
6. ኦብነግን በመደገፍ የሚገኝም ነገር አለ። ጋዝ ወይም ነዳጅ ነው። እ.አ.አ በ2009 በጄኔቫ አንድን የእንግሊዝ ኢምባሲ ሹመኛ ከሰዎች ጋር ሆነን አንገጋግረን ነበር። ኤርትራም ተሹሞ የሰራ ሰውና ስለ አካባቢው እውቀት ያለው ነው። ስለ ስብአዊ መብቶች ጉዳይ በኢትዮጵያ ገለጻ አደረግንለት። አላማችን በየአራት አመቱ አባል አገሮችን ስለ ስብአዊ መብቶች መሻሻልና ችግሮች በሚገመግመው የተባበሩት መንግስታት ጉባኤ ላይ (ዩኒቨርሳል ፕሮዴክ ሪቪው) የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ትኩረት እንዲያገኝ ለማድረግ ነበር። በጉባኤው ላይ አስተያየት ሰጭ አገሮች ከ5 ደቂቃ በላይ አይሰጣቸውም። ታዲያ እንግሊዙ የትኛውን የሰብአዊ ጥሰት አነሳ? በኦጋዴን ብቻ የተከሰተውን። በቃ። ሌላ ጥሰት ለወሬ ነጋሪም አልተሰማ። ቅዱስ ቫቲካን፣ሲዊዘርላንድ፣ሲውዴን፣ አውስትራሊያና ብራዚል በሚገባ በኢትዮጵያ ያለውን ችግር ለጉባኤው አስረድተዋል። የአሜሪካው ግን በጣም የተለየ ነበር። ኦባማ ገና በስልጣን የመጣበት ወቅት ስለነበር ለዴሞክራሲ መስፋፋት ተስፋ አልጨለመም ነበር። የአሜሪካው አምባሳደር የህወሃትን የጎሳ የበላይነት በጉባኤው ላይ ፍርጥ በማድረጉ፤ ሆዳሙ ፍሰሃ ገዳ ውሸት ነው ብሎ ቡራ ከረዩ ያለበት ትያትር ነበር ያየነው። ትእቢተኛው መለስ ዜናዊም ቀብጦ አምባሳደሩን ባለጌ ማለቱን አስታውሳለሁ።
7. ኦነግን በመደገፍና ኦሮሚያን በማስገንጠል ኦሮሞም ሆነ የውጭ ኃይሎች ምንም! ወላ ሃንቲ! የኢኮኖሚ ጥቅም አያገኙም። ባእዳን ዛሬ ካጋበሱት መሬት የበለጠ ኦነግ ኦሮሚያን መስርቶ ቢኮፈስ የበለጠ ጥቅም ሊያገኙ ይችላሉ? አይችሉም። ኦሮሞም እንደ አማራ አብሮ በደሙና በአጥንቱ በገነባት ኢትዮጵያ ሁሉ መብቱ ተከብሮ ነው መኖር የሚፈልገውም፤ የሚሻለውም።
7.1 ከተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ እየለዩ፤ ኦሮሞዎች ትናትም ሆነ ዛሬ ተጨቁኑዋል እየተባለ ጎልቶ በስብአዊ ድርጅቶች ሆነ በአለም አቀፍ ድርጅቶች የሚነገረው፤ የኦሮሞ ተቆርቁዋሪነቱ(ብሄረተኝነቱ) ገኖ ኢትዮጵያዊነቱ ተሙዋጥጦ ይጠፋል ከሚል ምኞት ነው። አቤ ቶኪቻው ይኼን ወዲያው ተገንዝቦ ማለፊያ አስተያየቱን እንዲህ ሲል ስንዝሮአል፤..”ስንቅ ያቀበሉ ኦሮሞ ያልሆኑም ታስረው እየማቀቁ ይገኛሉ።” የኦሮሞ ጥያቄ የሚባለው በተጨማሪም እንዲገን የሚደረገው አማራና ኦሮሞ እንዳይቀራረቡ ለማድረግና የወያኔን የግዛት ዘመን አደጋ እንዳይገጥመው ለመከላከል ነው። አማራና ኦሮሞ ተቀራርበው እንደ አምስቱ የአርበኞች ትግል(ጉራጌዎችም አሉበት) መዋጋት ከጀመሩ ህወሃት በግድ ይጠፋል። ይኼን እየተገነዘቡ፤ ብዙዎቹ የኦነግ ብሄረተኞች በአማራ ጥላቻ ስላበዱ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ለአድነታችን ጠላቶች መሳሪያ ሁነዋል። እነ ተስፋዬ ገ/አብና አንድናቂዎቻቸው አፈንዲ ሙተኪም የሚሰሩት ይኽንኑ ስራ መሆኑን አንብበናል። በጆራችን ስምተናል፡፡
7.2 ኢሳያስም ቢሆን እንዲህ እየባለገ በስልጣን ላይ እንዲቆይ የሚፈለገው፤ ኢትዮጵያን በማፍረሰ ቀመር ውስጥ ሊጠቅም ስለሚችል ነው። ዴምሄት 45 ሺህ የታጠቀ የትግሬ ጦር ነው። አቶ ጌታቸው ረዳ በትግርኛ ቁውንቁዋ ከተገኙ ምንጮች ሰሞኑን እንዳስነበበን፤ ትግርኝ ትግሪኝን ለመሰረት ኢሳያስ ያዋቀረው ጦር ነው። ሴቪ አድና ግን ከመሃከላችን ሆኖ ዴምሂት ወያኔን ለመጣል የሚታገል ጦር ነው ይለናል። የሚገርመው ሴቪ አድና አስብ የትግራይ ነው ሲል ጽፎኣል። ለነገሩ አስብ የአፋር ነው፡፡ የሚቀርበውም ለወሎ ነው። ትግራይ ትግርኝ ግን ግን አማራጩ ፕላን ወይም ፕላን ቢ ነው። ይቅናችሁ።
8. እንደመደምደሚያ፤ የሰው ልጅ የሚያመዛዝን አእምሮ ስላለው፤ እንኩዋን ለራሱ ለሰው ለእንሳስት ነፍስ ሲሳሳ አይተናል። ህወሃት ሰው በነገዱ አማራ ነህ እያለ መገደል የጀመረው በወልቃይት ጸገዴ ነው። እኛ ግን በስፋት የሰማነው መጀመሪያ በአርባጉጉ ነው። በአርባጉጉ አራጆቹ እርጉዝ ሴቶችን በሳንጃ ከመግደላቸው በፊት በጽንሱ ጾታ ፤ አማራ ወንድ? ወይስ ሴት? በማለት ይወራረዱ እንደነበርና ጡት ቆርጠው እስከማስበላት እንደደረሱ ራሳቸው ኦሮሞዎቹ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጽፈው ከሰጡት ደብዳቤ መረዳት ይቻላል።
8.1 አማራ ተገደለ! ራስህን ተከላከል እያልን የምንጮኸው በዘር ቆጠራ ተለክፈን አይደለም። እጅግ ስብአዊነት ስለሚሰማን እንጂ። እንሆ 23 አመታት ተቆጠሩ፤ ፕሮፌሰር ዓስራት ወልደየስ እንዳሉት ጠላቶቹ አማራ የሚሉትን ፈልገው ሲያጡት አናይም። ስንት አማራ እየጠፋ አምነስቲ ምን አለ? ምንም። የፕሮፈሰር መስፍን አማራ የለም ነገር፤ አማራን ከጥቃት ለመከላከል አላስቻለም።
8.2 ስብአዊ መብቶች ብዙ ናቸው። ዓማራ ተብሎ በተለያዩ መንገዶች ሲጠፋ፤ ጠፋ! ተፍናቀለ! ተገደለ ብለን ስንጮኽ የጎሳን ፖለቲካ ማራመድ ነው የሚሉን ስለሰብአዊነት የጠለቀ ግንዛቤ የሌላቸው ናቸው። ለነገሩ እውቀት እንደ አባት ስም አይወረሰም። ጥናትና ጥረት ያስፈልግዋል። አንዳንዶቹ ከተለያዩ ጎሳዎች በመወለዳቸው አማራ አምሮ ከተነሳ የትኛውን እንመርጣለን ብለውም የሚጨነቁ ቅይጥ-ጎሰኞች አሉ። እነዚህ ሰዎች ስብአዊነትን ከሁሉም በላይ መሆኑን የዘነጉ ናቸው። ለነገሩ በኢትዮጵያ ዳርቻ ካሉ ጎሳዎች በስተቀር ያልተቀላቀለ የለም። ስለዚህ በኢትዮጵያ የጎሳ ፖለቲካ አገርን ለመበዝበዝና ካልሆነም ለመበተን የሚካሄድ ስልታዊ ሃሳብ/አይዶሎጂ እንጂ በትውልድ ሃረግ የሚመዘን ጉዳይ አይደለም። እኛ አማራ ንጽህ ዘር ነው፤ የራሱን መንግስት ያቁም አላልንም። በአማራነቱ የሚደርሰበት ጥቃት በአገዛዙ እቅድ የሚደረግ ስለሆነ ራሱን ከጥፋት ያድን ነው የምንለው። ምንም እንኩዋን በቅርቡ ባሳተመው መጽሃፉ ስለ አማራ እልቂት አንድም ነገር ያልተነፈሰው ብርሃኑ እንክዋን በደረሰበት ትችትና፤ ይኼንኑ ጉዳይ በመገንዘብ ባለፈው መስከረም የኢትዮጵያ አዲስ አመት ምክንያት በማድረግ በአደረገው ንግግር አማራው በተለይ የጥቃት ኢላማ መደረጉን አምኖአል። ከአክሱም የተገኘው ጌታቸው ረዳ

የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ታሰሩ

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ

በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ለእሁዱ የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የታሰቱትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ለመጠየቅ ወደ ፖሊስ ጣቢያ የሄዱት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ታሰሩ፡፡

በቅስቀሳ ወቅት የነበሩት የሰማያዊ አባላትና አመራሮች መያዛቸውን ተከትሎ የእሁዱን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ለስበስባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ያሳወቁበትን ህጋዊ ደብዳቤ በመያዝ የአባላቱና አመራሩ እስራት ህገ ወጥ መሆኑን ለማስረዳትና አባላቱን ለመጠየቅ ወደ አራዳ መምሪያ ፖሊስ ጣቢያ ያቀኑት የሰማያዊ ፓርቲ የፋይንስ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ወሮታው ዋሴ እና የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊው አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል፡፡

1920593_613309012128094_4439816027396922242_n

በቅስቀሳ ላይ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች እየታሰሩ ነው

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር እሁድ ህዳር 7/2007 ዓ.ም ለሚያደርገው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ታሰሩ፡፡

የብሄራዊ ምክር ቤት አባል የሆነው አቶ ዮሴፍ ተሻገር እንዲሁም የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል የሆነው ሲሳይ በዳኔ መገናኛ አካባቢ ቅስቀሳ ላይ በነበሩበት ወቅት ታስረዋል፡፡

በተመሳሳይ የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ ሳምሶን ግዛቸው እንዲሁም የአዲስ አበባ ዞን ምክትል ሰብሳቢና ህዝብ ግንኙነት አቶ ማቲያስ መኩሪያ በአራዳ ክፍለ ከተማ ቅስቀሳ ላይ በነበሩበት ወቅት በፖሊስ ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ ታስረዋል፡፡

በሌሎች የአዲስ አበባ ክፍሎች ቅስቀሳ ላይ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች በፖሊስ ወከባ እየደረሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ህዳር 7/2007 ዓ.ም ቤልየር ሜዳ ላይ የሚደረገው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ሰማያዊ ፓርቲ የሚያስተብብረው ሲሆን በአንድ ወር የሚደረጉትን ሌሎቹን መርሃ ግብሮች 9ኙ ፓርቲዎች በየተራ እንደሚያሰተብብሩ መስማማታቸው ይታወቃል፡፡

10173740_613277408797921_4625849180036064757_n

ሊቀ ጳጳሱ ከስራና ወደ ውጭ አገር እንዳይወጡ ታገዱ (የዕግዱን ደብዳቤ ይዘናል)

$
0
0

Abune Yacob
የምስራቅ ኣፍሪካ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስና መቀመጫቸውን በደቡብ ኣፍሪካ ኣድርገው የነበሩት ብጹእ ኣቡነ ያዕቆብ ከሃገር አንዳይወጡና ከስራቸው መታገዳቸውን ለዘሐበሻ የደረሰው መረጃ ኣመለከተ፥፥ የዘሐበሻ ታማኝ ምንጮች ከነ ደብዳበው የላኩት መረጃ የሚከተለው ነው፥፥ ዝርዝሩን ይዘን አንመለሳለን፥፥
aba yakob
aba yakob 3

9ኙ ፓርቲዎች የጠሩት የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በኃይል ተበተነ

$
0
0

የተወሰደው እርምጃ የስርዓቱን ፍርሃት ደረጃ እንደሚያሳይ ኢ/ር ይልቃል ገለጹ
9ኙ ፓርቲዎች በትብብር የጠሩትን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በኃይል መበተኑ የስርዓቱ የፍርሃት ደረጃ ጫፍ መድረሱን ያሳያል ሲሉ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡

ኢንጅነር ይልቃል በተለይ ሰማያዊ ፓርቲ ከአሁን ቀደም እንደሚያደርገው ለምን እስከመጨረሻው አንበተንም አላላችሁም? ብለን ላቀረብንላቸው ጥያቄ ‹‹የአንድ ወር መርሃ ግብር አውጥተናል፡፡ ምርጫው ነጻና ፍትሓዊ እስኪሆን ድረስ የነጻነት ትግሉ የሚቀጥል ነው፡፡ በአራት ኪሎ አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ጠርተን ልናነጋግር በሞከርንበት ወቅት ብዙ እስርና ደብደባ ተፈጽሟል፡፡ ከዚህ የስርዓቱ ፍርሃት አንጻር ገና በመጀመሪያው ስራችን ወደኃይል እንዲገባ አልፈለግንም፡፡ ለሚቀጥሉት ስራዎቻችን ስንል ነው፡፡ ለሚቀጥለው ያንን በሚመጥን ደረጃ መዘጋጀት አለብን፡፡›› ብለዋል፡፡

ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት አክለውም ‹‹እኛ ዛሬ የአራት ኪሎን አካባቢ ሰዎች ነው የጠራነው፡፡ በዚህ ደረጃ ፈርተው ይህን ስብሰባ ያግዳሉ ብሎ ለመገመት ይከብዳል፡፡ ድሮውንም የሌላቸው የህዝብ ድጋፍ ጭራሹን እንደተሟጠ ነው የሚያሳየው፡፡ ትንሹም ነገር ለስልጣናቸው አስጊ ነው ብለው ማሰባቸው የፍርሃት ደረጃቸው ጫፍ እንደደረሰ ያሳያል፡፡›› ብለዋል፡፡

9 political parties

10687076_613770775415251_5729532920201734934_n
10407395_613772255415103_8496927474273177072_n

1002530_613770168748645_2259745416859937006_n

 

 

አንድነት ፓርቲ የ2007 ምርጫ በተቀናጀ ሁኔታ ለመምራት የምርጫ ግብረ ኃይል አቋቋመ

$
0
0

250283_729130643838539_4159739850168575891_nየአንድነት ፓርቲ ብሄራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በህዳር 6/2007 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ የ2007 ምርጫ በተቀናጀ ሁኔታ ለመምራት እንዲቻል 10 አባላት ያሉት በከፍተኛ የፓርቲው አመራሮች የሚመራ የምርጫ ግብረ ኃይል አቋቁሟል። ይህ የምርጫ ግብረ ኃይል ፓርቲው በ2007 ምርጫ ውጤታማ ሆኖ እንዲወጣ አጠቃላይ የምርጫ ዘመቻውን በበላይነት የሚመራ ሲሆን፤ በተጨማረም በቅርቡ የሚጀመረው የሚሊዮኖች ድምፅ ለፍትሀዊና ነፃ ምርጫ ህዝባዊ ንቅናቄ ዘመቻ ይህ ግብረ ኃይል የሚመራውና የሚያስተባብረው ይሆናል።
በዚህ አጋጣሚ አንድነት ለምርጫው ከፍተኛ ዝግጅት በማደረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን ከዚህ በፊት ተጀምሮ የነበረው የሚሊዮኖች ድምፅ ዘመቻ የመጨረሻው ምዕራፍ የሆነው ለፍትሀዊና ነፃ ምርጫ ህዝባዊ ንቅናቄ ግቡን እንዲመታና የምርጫ ምህዳሩን እንዲሰፋና ለሁሉም ተወዳዳሪዎች የተመቻቸ እንዲሆን ለምናደርገው ትግል ህዝቡ ከጎናችን በመቆም ነፃነትና ዴሞክራሲያዊ ለውጥ በሀገራችን ለማስፈን ቆርጦ እንዲነሳ ጥሪያችን እናስተላልፋለን።

 


Health: ሴቶችን በከፍተኛ ሁኔታ የሚያጠቁት 10 የካንሰር ዓይነቶችና መከላከያዎቻቸው

$
0
0

‹‹ሴቶችን በከፍተኛ ደረጃ ስለሚያጠቁት የካንሰር አይነቶችና ስለመከላከያዎቻቸው በሚገባ ማወቅ እፈልጋለሁ››

ከሁሉ አስቀድሜ የማክበር ሰላምታዬን እያቀረብኩ ለማቀርብላችሁ ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ እንደምትሰጡኝ በመተማመን ነው፡፡ 

በእርግጥ እስካሁን ድረስ ሙሉ በሙሉ ጤነኛ ነኝ፡፡ ይሁን እንጂ እናቴ ከ5 ዓመት በፊት ማለትም የ16 ዓመት ታዳጊ በነበርኩበት ጊዜ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው በማህፀን ካንሰር መሆኑን ማወቄ በአጠቃላይ ለሴቶች ጠንቅ ስለሆኑት ካንሰሮች የማወቅ ፍላጎት እንዲኖረኝ አድርጎኛል፡፡ ስለ ገዳዮቹ ካንሰሮች ማወቀ ብቻ ሳይሆን በእነኚህ የካንሰር አይነቶች እንዳልጠቃ ቅድመ ጥንቃቄ ለማድረግም እፈልጋለሁ፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች ባሰፈርኳቸው ጥያቄዎች ዙሪያ ባለሙያዎችን በማማከር ጭምር ተገቢውን ምላሽና ማብራሪያ እንድትሰጡኝ እጠይቃለሁ፡፡ 

1. ሴቶችን በከፍተኛ ደረጃ ስለሚያጠቃቸው የካንሰር አይነቶች

2. እኔም ሆንኩ ሌሎች በእነኚህ ካንሰሮች እንዳንጠቃ ማድረግ ስለሚኖርብን ጥንቃቄ

በአጠቃላይ ለሴቶች ጠንቅ ስለሆኑት የካንሰር አይነቶችና ስለመከላከያዎቻቸው በቂ የሆነ ማብራሪያ እንድትሰጡኝ እየጠየኩ፣ ዕድሜዬም 21 መሆኑን እገልፃለሁ፡፡ 

(ራሄል አበበ ነኝ)

Endometrial-Cancer

ምላሽ፡- ካንሰር በአብዛኛው ከቤተሰብ የህክምና ታሪክ፣ ከምንከተለው የህይወት ዘይቤ እና ምርጫ እንዲሁም ከአካባቢው ሁኔታዎች ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በእርግጥ በቤተሰባዊ የጤና ታሪክ ምክንያት የሚከሰትን ካንሰር ለመቆጣጠር እጅግ አስቸጋሪ ነው፡፡ በአካባቢ ሁኔታዎች ምክንያት የሚከሰተው ካንሰርም ቢሆን የመከላከል ዕድላችን አነስተኛ ነው፡፡ ይሁን እንጂ እንደ አመጋገብ፣ ክብደት፣ የእንቅስቃሴ ሁኔታ፣ ሲጋራ ማጨስና በመሳሰሉት ከአኗኗር ዘይቤ ጋር የተያያዙ ካንሰሮችን ለመከላከል ግን እንችላለን። ይህም ማለት ጤናማ የሆነ የአኗኗር ዘይቤ ካንሰርን ለመከላከል ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ማለት ነው፡፡

‹‹ካንሰርን የመከላከል እርምጃዎች በአብዛኛው በራሳቸው በሰዎቹ እጅ የወደቀ ነው፡፡ ሰዎች ብርቱ ጥንቃቄን ካደረጉ ራሳቸውን ከካንሰርም ሆነ ከሌሎች ከማናቸውም በሽታዎች መከላከል ይችላሉ›› ያሉት በኒውዮርክ ሲቲ በሚገኘው የስሎአን ኬተርንግ መታሰቢያ የካንሰር ማዕከል ውስጥ በጃይኖኮሎጂ የህክምና ዘርፍ ስፔሻል ሐኪም የሆኑት ሪቻርድ ባራካት ናቸው፡፡

እስካሁን ባለው ሁኔታ ከሶስት ሴቶች መካከል ሁለቱ በካንሰር የመያዝ ዕድል አይገጥማቸውም፡፡ ይህም ሆኖ ካንሰር በዓለማችን ውስጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሴቶችን ያጠቃል፣ ይገድላልም፡፡ በ2008 ብቻ በአሜሪካ ውስጥ ከ700,000 በላይ የሆኑ ሴቶች በካንሰር በሽታ ተጠቅተዋል። ሴቶችን በከፍተኛ ደረጃ ከሚያጠቁት የካንሰር አይነቶች ደግሞ ከዚህ በታች የተጠቀሱት አምስቱ በዋነኝነት የሚጠቀሱና በገዳይነታቸውም የሚታወቁ ናቸው፡፡

1. የጡት ካንሰር (Breast cancer)

ይህ የካንሰር አይነት ከሴቶች የካንሰር ጉዳዮች 20 በመቶውን ሲሆን በየዓመቱ በካንሰር ምክንያት ከሚሞቱት ሴቶች መካከል 15 በመቶ የሚሆኑትን የሚገድለው ይኸው የካንሰር አይነት መሆኑን ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ ከ8 ሴቶች መካከል አንዷ በዚህ የካንሰር አይነት እንደምትጠቃም ተረጋግጧል፡፡

2. የሣንባ እና የመተንፈሻ አካላቶች ካንሰር (Lung and bronchus cancers)

በሴቶች ላይ ከሚከሰቱት የካንሰር አይነቶች ውስጥ 14 በመቶ የሚሆኑት የሚጠቁት በሣንባ እና በመተንፈሻ አካላቶች ካንሰር መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ በየዓመቱ በካንሰር ከሚሞቱት ሴቶች መካከል 26 በመቶ የሚሆኑት ሟቾች ህመም ከዚሁ የካንሰር አይነት ጋር የተያያዘ እንደሆነም ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ ከ16 ሴቶች መካከል አንዷ በዚሁ የካንሰር አይነት ትጠቃለች፡፡

3. የትልቁ አንጀትና የፊንጢጣ ካንሰር (Colon and rectal cancers)

በሴቶች ላይ ከሚከሰቱት የካንሰር ህመሞች ውስጥ 10 በመቶ የሚሆኑት ከትልቁ አንጀትና ከፊንጢጣ ካንሰር ጋር የተያያዙ ሲሆኑ ከካንሰር ሟቾች መካከል 9 በመቶ የሚሆኑትም በዚሁ የካንሰር አይነት የሚከሰት እንደሆነ ተረጋግጧል፡፡ በየዓመቱ በካንሰር ከሚሞቱት ሴቶች መካከል 26 በመቶ የሚሆኑት ሟቾች ህመም ከዚሁ የካንሰር አይነት ጋር የተያያዘ እንደሆነም ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ ከ16 ሴቶች መካከል አንዷ በዚሁ የካንሰር አይነት ትጠቃለች፡፡

4. የማህፀን ካንሰር (Uterine cancer)

በሴቶች ላይ ከሚከሰቱት የካንሰር አይነቶች መካከል 6 ከመቶ የሚሆኑት የሚጠቁት በዚሁ የካንሰር አይነት ነው፡፡ በካንሰር ህመም ከሚሞቱት ሴቶች መካከል 6 ከመቶ የሚሆኑት ደግሞ ህመማቸው ከዚሁ የካንሰር አይነት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ከ41 ሴቶች መካከል አንዷ በዚሁ የማህፀን ካንሰር አይነት እንደምትጠቃም ተረጋግጧል፡፡

5. የነጭ የደም ሴል ካንሰር 

በካንሰር ህመሞ ከሚጠቁ ሴቶች መካከል 4 በመቶ የሚሆኑት ህመማቸው ከዚህ የካንሰር አይነት ጋር የተያያዘ ነው። በካንሰር ምክንያት ከሚሞቱት ሴቶች መካከል ደግሞ 3 ከመቶ የሚሆኑት የመሞታቸው ምክንያት ይኸው የነጭ የደም ሴል ካንሰር አይነት ሲሆን ከ53 ሴቶች መካከል አንዷ በዚሁ የካንሰር አይነት እንደምትጠቃም ጥናቶች አረጋግጠዋል፡፡

6. የጡት ካንሰር

የጡት ካንሰር ሴቶችን በከፍተኛ ደረጃ ከሚያጠቁት የካንሰር አይነቶች መካከል በዋናነት የሚጠቀስ ሲሆን ለዚህ ካንሰር መከሰት በዋነኛነት የሚጠቀሱት ምክንያቶችም የሚከተሉት ናቸው፡፡

ዕድሜ፡- በጡት ካንሰር ከሚጠቁት ሶስት ሴቶች መካከል ሁለቱ ዕድሜያቸው ከ55 በላይ ነው፡፡

ቤተሰባዊ ታሪክ፡- አንዲት ሴት እናቷ፣ እህቷ ወይም ልጇ በጡት ካንሰር የተያዘች ከሆነ እሷም በዚህ ካሰር የመያዝ እድሏ እጥፍ ይሆናል፡፡

የቆዳ ቀለም፡- ጥቁር ቀለም ያላቸው ሴቶች በጡት ካንሰር አንዴ ከተያዙ የመሞት ዕድላቸው ከፍተኛ እንደሆነ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ ይህም ሆኖ ካንሰሩ ብዙውን ጊዜ ከጥቋቁር ሴቶች ይልቅ የሚያጠቃው ነጭ ቀለም ያላቸውን ሴቶች ነው፡፡ ምክንያቱም የነጮቹ ዕጢ በፍጥነት የሚያድግ በመሆኑ ነው፡፡

የጡት ህብረ ህዋሳት፡-  የጡት ህብረ ህዋሳት አጀብ ብለው በብዛት የሚገኙ ከሆነ ሴቶች በጡት ካንሰር የመያዝ ዕድላቸው ከፍተኛ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡

የጨረር ህክምና፡- ሴቶች ቀደም ሲል በደረታቸው አካባቢ የጨረር ህክምና አድርገው ከሆነ ዘግየት ብሎ በጡት ካንሰር ሊጠቁ ይችላሉ፡፡

– ከ12 ዓመት በፊት እና ከ55 ዓመት በኋላ የወር አበባ የሚያዩ ሴቶች በዚህ የካንሰር አይነት የመጠቃት ዕድላቸው ከፍ ይላል፡፡

– የሚያረግዙ ወይንም ከ30 ዓመታቸው በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያረግዙ ሴቶች በጡት ካንሰር ሊጠቁ እንደሚችሉ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

– የወሊድ መከላከያ እንክብሎችን መጠቀም ሌላው የጡት ካንሰርን የሚያስከትል ነገር ነው፡፡

– ለልጆቻቸው ጡትን የማያጠቡ

– ከመጠን በላይ የወፈሩ እና ቅባት የበዛባቸውን ምግቦች የሚያዘወትሩ

– በየቀኑ የአልኮል መጠጦችን በብዛት የሚጎነጩ (የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ጥናት እንደሚያመለክተው ለሰባት ዓመታት ያህል በሳምንት ሶስት ቀን አልኮል ሲጠጡ የነበሩ 1.3 ሚሊዮን ሴቶች ውስጥ አብዛኛዎቹ ለጡት ካንሰር ተጋልጠዋል)

– ፅንስ ካስወረዱ በኋላ በዚሁ ምክንያት የሚከሰተውን ሕመም ለማስወገድ ዳሶታይል ስቲበርስትሮል (DES) የተባለውን መድሃኒት የሚጠቀሙ።

– የወር አበባ መታየት ካቆመ በኋላ (ከ50 ዓመት በላይ) የሚደረግ የሆርሞን ህክምና፡፡

ለጡት ካንሰር መከሰት በዋነኛነት የሚጠቀሱት ምክንያቶች እንደሆኑ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡

7. የሣንባ እና የመተንፈሻ አካላት ካንሰር

እጅግ ገዳይ ናቸው ከሚባሉት የካንሰር አይነቶች መካከል በዋነናነት የሚጠቀሰው የሣንባ ካንሰር ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህንን የካንሰር አይነት በቀላሉ መከላከል ይቻላል። የሣንባ ነቀርሳ ካለባቸው ሴቶች መካከል 80 ከመቶ የሚሆኑት እንዲሁም ከወንዶች ውስጥ 90 ከመቶ የሚሆኑት ሲጋራ ማጨስን በማቆም ብቻ ራሳቸውን ከዚህ ካንሰር ነፃ ማድረግ ይችላሉ፡፡ ሲጋራ የሚያጨሱ ሰዎች በሣንባ ካንሰር የመያዝ ዕድላቸው ከማያጨሱት ከ10 እስከ 20 ጊዜ በላይ የሰፋ ነው፡፡ ሌሎቹ ለሣንባ እና ለመተንፈሻ አካላት ካንሰር የሚያጋልጡት ምክንያቶች ደግሞ፡-

– ከሚያጨሱ ሰዎች ጋር መዋልና ማደር

– ራይን ጋዝ

– ኃይለኛ መርዝ (Arsenic)

– ሬንጅ (Tar)

– ጥላሸት (Soot)

ጤናማ የሆኑ አመጋገብ፣ የአልኮል መጠጥ መቀነስና የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በእቅድ ማከናወን በሣምባ እና በመተንፈሻ አካል ካንሰር የመያዝ አጋጣሚን ይቀንሳል፡፡

8. የትልቁ አንጀት እና የፊንጢጣ ካንሰር

በትልቁ አንጀት እና በፊንጢጣ ካንሰር ከሚጠቁት ሴቶች መካከል 90 ከመቶ የሚሆኑት ዕድሜያቸው ከ50 በላይ ነው። ለዚህ የካንሰር አይነት የሚያጋልጡት ምክንያቶች ደግሞ፡-

– የግለሰቡ ወይም የቤተሰብ ከአንጀት ካንሰር ጋር የተያያዘ ህክምና በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ትናንሽ ነፍሳት፣ የሰውነት እብጠትና የሆድ ዕቃ ህመም

– ልፍስፍስነት፣

– ሲጋራ ማጨስ

– የአልኮል መጠጦች ሱሰኝነት

– ከመጠን በላይ ሥጋ እና ስብነት የበዛባቸው ምግቦችን መመገብ እና አነስተኛ መጠን ያላቸው አትክልትና ፍራፍሬዎችን መውሰድ ናቸው፡፡

ይህንን የካንሰር አይነት ለመከላከል ቁልፉ ዘዴ በየጊዜው ምርመራ ማድረግ እና ፈጣን የመከላከል እርምጃ መውሰድ ናቸው። ትልቁ አንጀት እና ፊንጢጣ ከተጠቃ በኋላ የተጠቁት ሴሎች በአንጀት ውስጥ ለማደግ ከ10 እስከ 15 ዓመት ሊፈጅባቸው ይችላል፡፡ በመሆኑም በየጊዜው የአንጀትና የፊንጢጣ ምርመራ የምናደርግ ከሆነ ችግሩ ወደ ካንሰርነት ከመቀየሩ በፊት ልንከላከለው እንችላለን፡፡

በቅርቡ የአሜሪካው ብሔራዊ የጤና ኢንስቲቲዩት ባሰራጨው ዘገባ ደግሞ ካልሲየም እና የወተት ተዋፅኦ ምግቦች የአንጀትና የፊንጢጣ ካንሰርን ለመከላከል እንደሚያስችሉ ጠቁሟል። የጤና ኢንስቲቲዩት በ200,000 ወንዶችና በ200,000 ሴቶች ላይ ባካሄደው ለሰባት ዓመታት የዘለቀ ጥናት ካልሲየም የበዛባቸውን ምግቦች በየጊዜው መመገብ ይህንን የካንሰር አይነት ለመከላከል እንደሚያስችል አረጋግጧል፡፡

9. የማህፀን ካንሰር

ለማህፀን ካንሰር መከሰት በዋነኛነት የሚጠቀሰው ምክንያት የሆርሞን ለውጥ ነው፡፡ በተለይም ከአስትሮጂን ጋር የተያያዘ የሆርሞን ለውጥ ይህንን የካንሰር አይነት ሊያስከትል እንደሚችል ተረጋግጧል። በእንግሊዝኛ Uterine cancer ወይም Endometical ተብሎ ለሚጠራው የማህፀን ካንሰር በዋነኛነትና በመንስኤነት የሚጠቀሱት ምክንያቶች፡-

– ከተለመደው አማካይ በላቀ ሁኔታ የወር አበባ መደጋገም

– ለማርገዝ ያለመቻል

– የኤስትሮጂን ህክምና መውሰድ

– ከመጠን በላይ መወፈርና ቅባት የበዛባቸውን ምግቦች በብዛት መመገብ

– ለጡት ካንሰር የሚወሰደውን ታሞክሲፈን የተባለውን መድሃኒት በፊትም ሆነ በአሁኑ ወቅት መውሰድ

– የትናንሽ ዕጢዎች በማህፀን ውስጥ መከሰት

– የዕድሜ መግፋት

– የስኳር ህመም

– ከአንጀት ካንሰር ጋር የተያያዘ ቤተሰባዊ የህመም ታሪክ

– ከጡት ወይም ከኦቫሪያን ካንሰር ጋር የተያያዙ ግላዊ ታሪክ

– የማህፀን ግድግዳ መወፈር ናቸው፡፡

10. የነጭ የደም ሴል ካንሰር

ይህ የካንሰር አይነት በነጭ የደም ሴል ውስጥ የሚከሰት ሲሆን የተፈጥሮ የመከላከል አቅምን በማውረድ በቆሽት፣ በጉሮሮ እና በአጥንት መቅኔ ውስጥ ካንሰር እንዲከሰት የሚያደርግ ነው፡፡ ለዚህ የካንሰር አይነት የሚያጋልጡት ምክንያቶች ደግሞ፡-

– የተዳከመ ተፈጥሯዊ የመከላከል አቅም

– ዕድሜ፡- በዚህ የካንሰር አይነት ከሚጠቁት ሰዎች መካከል አብዛኛዎቹ ዕድሜያቸው ከ60 ዓመት በላይ ነው፡፡

– ለፀረ ተክል እና ለፀረ ነፍሳት የሚሆኑ መድሃኒቶችን ለመሳሰሉት ኬሚካሎች መጋለጥ

– የተፈጥሮ የመከላከል አቅምን የሚያጠቁ ህመሞች

በነጭ የደም ሴል ካንሰርን ለማስወገድ ወይም ለመከላከል የሚያስችል ዘዴ እስካሁን ድረስ አልተገኘም፡፡ ይሁን እንጂ እንደ ኤች.አይ.ቪ የመሳሰሉትን ተፈጥሯዊ የመከላከል አቅምን ከሚያሳጡ በሽታዎች ራስን መጠበቅ ከነጭ የደም ካንሰር ለመታደግ ያስችለናል፡፡ ምክንያቱም ይህንን የካንሰር አይነት ከሚያስከትሉት ህመሞች አንዱ ኤች.አይ.ቪ በመሆኑ ነው፡፡

ማጠቃለያ፡- የአኗኗር ዘይቤን በመቀየርና በማሻሻል፣ የአመጋገብ ለውጥን የመሳሰሉ ቀላል ለውጦችን በመፍጠርና በየጊዜው የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በማድረግ ከማንኛውም የካንሰር አይነት ራሳችንን ለመታደግ እንችላለን፡፡ ሴቶችን በማጥቃት ገዳይ ከሆኑት የካንሰር አይነቶች ደግሞ ከላይ የተጠቀሱት በዋነኝነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ አምስቱን ገዳይ የካንሰር አይነቶች በዚህ መልኩ ካቀረብን ዘንድ ከማህፀን ካንሰር ጋር የሚያያዘውን የማህፀን አፍ ካንሰር በሚመለከት ደግሞ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡

ማህጸን በእንግሊዝኛ (Uterus or womb) ተብሎ የሚጠራ እና በሴቶች ሆድ ውስጥ በፊኛ እና ፊንጢጣ መካከል የሚገኝ ደግሞም ሾጠጥ ያለ ቅርፅ ያለው ኦርጋን ነው፡፡ ይህ አካል ሴቶች በእርግዝና ወቅት ፅንሱ እስኪወለድበት ጊዜ ድረስ የሚያድግበት ነው፡፡

ማህፀን በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል፡፡ እነሱም የማህፀን አፍ (Cervix or Mouth of uterus) እና ፅንሱን የሚይዘው አካል (corpus or body) የሚባሉት ናቸው፡፡ ኮርፐስ ማለትም ፅንሱን የሚታቀፈው አካል በማህፀን ገበር እና በጡንቻማ ህብረ ህዋሳት የሚዋቀር ነው። አብዛኛው የማህፀን ካንሰር የሚከሰተው ደግሞ በውስጣቸው ገበር ውስጥ መሆኑን ጥናቶች አረጋግጠውታል፡፡

በአሜሪካ በምትገኘው የኒውዮርክ ግዛት ውስጥ የማህፀን ካንሰር ሴቶችን በከፍተኛ ደረጃ ከሚያጠቁት የካንሰር አይነቶች በ4ኛ ደረጃ የሚገኝ ነው፡፡ በየዓመቱ በዚህ ግዛት ውስጥ ከ3600 ሴቶች በላይ የሚሆኑት በዚህ የካንሰር አይነት እንደሚጠቁና 600 የሚሆኑት ደግሞ እንደሚሞቱ መዘገቡ የማህፀን ካንሰር ምን ያህል አደገኛ መሆኑን የሚያንጸባርቅ ነው፡፡

የማህፀን ካንሰር የሚያጠቃው የትኞቹን ሴቶች ነው?

አብዛኛዎቹ በማህፀን ካንሰር የሚጠቁት ሴቶች ዕድሜያቸው ከ45 ዓመት በላይ ነው፡፡ ይህ አይነቱ ካንሰር ብዙውን ጊዜ የሚያጠቃው ዕድሜያቸው ከ45 እስከ 65 ባሉት ሴቶች ላይ ሲሆን ከጥቁር ሴቶች ይልቅ በነጭ ሴቶች ላይ እንደሚበረታም ተረጋግጧል፡፡

ለማህፀን ካንሰር መንስኤ የሚሆኑት ምንድናቸው?

በአሁኑ ወቅት ለማህፀን ካንሰር በዋነኛነት የሚጠቀሱት ምክንያቶች በግልፅ የሚታወቁ አይደሉም፡፡ ይሁን እንጂ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ምክንያቶች ለአንዲት ሴት በዚህ አይነቱ ካንሰር መያዝ በምክንያትነት ሊጠቀሱ እንደሚችሉ ሳይንቲስቶች ተስማምተውበታል፡፡

– የሆርሞን መዛባት፡- በአነስተኛ ዕድሜ የወር አበባን የሚያዩ፣ በጣም ዘግይተው የወር አበባ ማየትን የሚያቆሙ (የሚያርጡ)፣ አርግዘው የማያውቁ፣ የሙሉ ጊዜ እርግዝና ያላጋጠማቸው ወይም ጥቂት ልጆችን ብቻ የወለዱ ሴቶች በማህፀን ካንሰር የመያዝ ዕድላቸው ከፍ ያለ ነው፡፡

– የቤተሰብ ታሪክ፡- እናቶቻቸው፣ እህቶቻቸው ወይም ሴት ልጆቻቸው በማህፀን ካንሰር የተጠቁ ሴቶች እነሱም በዚህ በሽታ የመያዝ ዕድል ሊገጥማቸው እንደሚችል ጥናቶች አረጋግጠዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቤተሰብ አባሎቻቸው በአንጀት ካንሰር የተጠቁ ሴቶች በማህፀን ካንሰር የመያዝ ዕድል ሊገጥማቸው እንደሚችል ጥናቶች ጠቁመዋል፡፡

ከመጠን በላይ መወፈር፡- ከልክ በላይ የሚወፍሩ ሴቶች በማህፀን ካንሰር ሊያዙ ይችላሉ፡፡

የጨረር ህክምና፡- በሌላ የካንሰር አይነት ህመም ምክንያት በዳሌያቸው አካባቢ የጨረር ህክምና ያደረጉ ሴቶች በማህፀን ካንሰር የመያዝ ዕድል ሊገጥማቸው ይችላል፡፡

ያልተመጣጠነ የሴታሴትነት ጾታዊ ሆርሞን፡- በህክምናው ቃል ፖሊሳይስቲክ ኦቫሪ ሲንድረም (polycystic ovary syndrome (PROS)) የሚለው የሆርሞን መዛባት አይነት ሴቶች ያልተመጣጠነ የሴታሴትነት ጾታዊ ሆርሞን (imbalance of female sex hormones) በሚገጥማቸው ጊዜ የሚከሰት ሲሆን ይህም ሁኔታ የወር አበባ ዑደት መዛባትን፣ በዕንቁላል ማፍሪያቸው አካባቢ ውሃ የቋጠረ እብጠትን፣ ለማርገዝ ያለመቻልንና ሌሎችንም የጤና እክሎችን ያስከትላል፡፡ ከሁሉም በላይ ያልተመጣጠነ የሴታሴትነት ፆታዊ ሆርሞን ያለባቸው ሴቶች የማህፀን ካንሰር እንደሚገጥማቸው ተረጋግጧል፡፡

የሆርሞን ተጠቃሚነት፡- አንዳንድ ሴቶች በወር አበባ ጊዜያቸው መዛባት ምክንያት ሆርሞኖችን ለመተካት የሚያስችል የህክምና አይነትን ይጠቀማሉ፡፡ ይህ የሆርሞን ህክምና ደግሞ የማህፀን ካንሰርን ሊያስከትል እንደሚችል ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ ይህም ሆኖ የወሊድ መከላከያ እንክብሎች በማህፀን ካንሰር የመያዝን አደጋ ይቀንሱታል፡፡

ታሞክሲፊን፡- የጡት ካንሰርን ለመከላከል የሚወሰድ የመድሃኒት አይነት ሲሆን ይህንን የመድሃኒት አይነት ለረዥም ጊዜ የሚጠቀሙ ሴቶች በማህፀን ካንሰር የመያዝ ዕድላቸው ከፍ ያለ ነው፡፡

ሌሎች ለማህፀን ካንሰር መከሰት የሚጠቀሱት ምክንያቶች

በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም የሚገኙት ታዋቂ ሳይንቲስቶች ለማህፀን ካንሰር መከሰት በዋነኝነት የሚጠቀሱ መንስኤዎችን ለማግኘት ከፍተኛ ጥናት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ እስካሁን በተደረጉት ጥናቶች መሰረት ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ ያልተመጣጠነ ምግብ መመገብ፣ ሲጋራ ማጨስ፣ አልኮል መጠጣትና የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ያለማድረግ ለማህፀን ካንሰር መከሰት በምክንያትነት የሚጠቀሱ ነጥቦች መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የስኳር ህመምተኛ የሆኑ ሴቶች እና በፓፒሎማ ቫይረስ የተጠቁ ሴቶች በማህፀን ካንሰር የመያዝ ዕድላቸው ከፍ ያለ ነው፡፡

የማህፀን አፍ ካንሰር 

የማህፀን አፍ በማህፀን ታችኛው ክፍል የሚገኝ ሲሆን ፈረንጆች ይህንን የማህፀን ክፍል አንዳንዴ ዩተረን ሴርቪክስ ብለው ይጠሩታል፡፡ ይህ የማህፀን ክፍል ማህፀንን ከብልት ጋር የሚያገናኝ ነው፡፡ ለሰውነት አካል ቅርብ የሆነው የማህፀን አፍ ደግሞ ኢንዶሴርቪክስ ተብሎ ይጠራል። ከብልት ቀጥሎ የሚገኘው የማህፀን አፍ አካል ኤክሶ ሰርቪክስ ወይም ኤክቶሰርቪክስ ይባላል፡፡

የማህፀን አፍን ሸፍነው የሚገኙት ሁለቱ ሴል አይነቶች ሶክዋሞሴልስ እና ግላንዱላር ሴልስ ተብለው የሚጠሩ ናቸው፡፡ እነኚህ ሁለት የሴል አይነቶች የሚገናኙበት ቦታ ደግሞ ትራንስፎርሜሽን ዞግ ተብሎ ይጠራል፡፡ አብዛኛው የማህፀን አፍ ካንሰር የሚከሰተውም በዚሁ ቦታ ላይ ነው፡፡

አብዛኛዎቹ የማህፀን አፍ ካንሰር የሚጀምሩት በማህፀን አፍ ገበር ላይ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ሴሎቹ በድንገት ወደ ካንሰርነት የሚለወጡ አይደሉም፡፡ መደበኛ የሆኑት የካንሰር አይነቶች መጀመሪያ ቀስ በቀስ ወደ ቅድሞ ካንሰርነት መለወጥ ይጀምራሉ፡፡ የህክምና አዋቂዎች ይህንን የሴሎች የቅድመ ካንሰር ለውጥ በተለያየ ስም ይጠሩታል፡፡ ከእነኚህም መገለጫዎች መካከል ሰርቪካል ኢንትራኢፒቴሊያል፣ ስክዋሞስ ኢንትራኢፒቴሊያል ሌዝዩን እና ዳይስፕላዚያ ናቸው፡፡ ይሁንና እነኚህ የቅድመ ካንሰር ለውጦች በምርመራ ማወቅና በህክምና ካንሰር እንዳይዘን መከላከል እንችላለን፡፡

የማህፀን አፍ ካንሰር እና የቅድመ የማህፀን አፍ ካንሰሮች ምን አይነት ገፅታ እንዳላቸው በማይስክሮኮፕ እይታ መረዳት ይቻላል፡፡ የማህፀን አፍ ካንሰር በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች የሚከፈል ነው፡፡ እነኚህም ስኩዋሞስ ሴል ካርሲኖማ እና አዴኖካርሲኖማ ተብለው የሚጠሩ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ከማህፀን አፍ ካንሰሮች ውስጥ ከ80-90 በመቶ የሚሆኑት ስኩዋሞስ ሴል መሆናቸው በጥናት ተረጋግጧል፡፡

ስኩዋሞስ ሴል ካርኪኖማ የተባለው የማህፀን አፍ ካንሰር አይነት ብዙውን ጊዜ የሚከሰተው ኤክሶሰርቪክስ እና ኢንዶሰርቪክስ በሚገናኙበት ቦታ ላይ ነው።

ሌሎቹ የማህፀን አፍ ካንሰሮች ደግሞ ብዙውን ጊዜ አዴኖካርሲኖማ ተብለው የሚታወቁት ናቸው፡፡ የማህፀን አፍ አዴናካርሲኖማስ ላለፉት 20 እና 30 ዓመታት የተለመዱ ሆነዋል፡፡ ይህ የማህፀን አፍ ካንሰር የሚከሰተው ደግሞ ሙከስ ግላንድ ሴልን በሚያመርትበት በአዲኖካርሲሞናስ ውስጥ ነው፡፡

ምንም እንኳን የማህፀን አፍ ካንሰር ብዙውን ጊዜ በቅድመ ካንሰር የለውጥ ሂደት የሚከሰት ቢሆንም የቅድመ ካንሰር ለውጥ ከታየባቸው ሴቶች ውስጥ በካንሰሩ የሚጠቁት ጥቂቶቹ ብቻ ናቸው። ከቅድመ የማህፀን አፍ ካንሰር ወደ ዋናው የማህፀን አፍ ካንሰር ያለው ሂደት በርካታ ዓመታትን ይወስዳል፡፡ ይህም ሆኖ አንዳንዴ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ዋናው ካንሰር ሊከሰትም ይችላል፡፡ በብዙዎች ሴቶች የቅድመ ካንሰር ሴሎች ያለ ምንም የህክምና ክትትል ሊወገዱ የሚችሉ ናቸው፡፡ በአንዳንድ ሴቶች ግን ቅድመ ካንሰሩ ወደ እውነተኛውና ገዳዩ ካንሰርነት ሊቀየር ይችላል፡፡ በመሆኑም በቅድመ ካንሰር የለውጥ ጊዜ ውስጥ የሚደረግ ምርመራ እና የህክምና ክትትል ዋናው ካንሰር እንዳይከሰት ሊያደርግ ይችላል፡፡

የቅድመ ካንሰር ለውጦች በማህፀን ውስጥ እንደሚገኙት የሴል አይነቶች ሁኔታ የተለያዩ ናቸው፡፡ ይህንን የለውጥ ሂደት ማወቅ የሚቻለው ደግሞ በማይስክሮኮፕ አማካኝነት ሴሎችን በመመልከትና በመመርመር ነው፡፡

Endometrial-Cancerየማህፀን አፍ ካንሰርን መከላከል ይቻላል?

በአብዛኛው ዋና ዋናዎቹ የማህፀን አፍ ካንሰሮች በቅድመ ካንሰር ለውጥ የሚከሰቱ በመሆናቸው ይህ የካንሰር አይነት እንዳይስፋፋ ማድረግ የሚቻልባቸው ሁለት መንገዶች አሉ፡፡ የመጀመሪያው ዘዴ የቅድመ ካንሰሩን ሂደት በማወቅ ወደ ዋና ካንሰርነት እንዳይቀየሩ መከላከል ሲሆን ሁለተኛው መንገድ ደግሞ የቅድመ ካንሰር ለውጡ እንዳይከሰት በመከላከል ነው፡፡

የማህፀን አፍ ካንሰርን ለመከላከል ዋነኛው ዘዴ ካንሰሩ ወይም ቅድመ ካንሰሩ መኖሩን በምርመራ በማረጋገጥ እንዲወገድ በማድረግ ነው፡፡ በተለይም የቅድመ ካንሰሩ ለውጥ ወደ ዋናው ካንሰርነት እንዳይለወጥ መከላከል እጅግ ጠቀሜታነት አለው፡፡

ዋና ዋና ምክሮች

– እያንዳንዷ ሴት ዕድሜዋ 21 ዓመት ከሞላበት ጊዜ ጀምሮ የማህፀን አፍ ምርመራ ማድረግ ይኖርባታል፡፡ ዕድሜያቸው ከ21-29 የሆኑ ሴቶች ቢያንስ በየሦስት ዓመቱ ምርመራ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡

– ከ30 ዓመታቸው ጀምሮ የHPV እና የPAP ምርመራዎችን በቅንጅት ቢያንስ በየአምስት ዓመቱ ማድረጋቸው አስፈላጊ ነው፡፡

– ሌላው አማራጭ ደግሞ ዕድሜያቸው ከ30 እስከ 65 የሆኑት ሴቶች የPAP ምርመራን ብቻ በየሶስት ዓመቱ ማድረግ ያለባቸው መሆኑ ነው፡፡

በአጠቃላይ የማህፀን አፍ ካንሰርን መከላከል የሚቻለው በአብዛኛው ሂደቱ ከቅድመ ካንሰርነት ወደ ዋናው ካንሰርነት ከመለወጡ በፊት ቢሆን ይመረጣል ይላሉ የህክምና ባለሙያዎቹ፡፡

ፖሊስ እና ደህነንቶች የዛሬውን ሰልፍ መበተናቸው የስርዓቱን ፍርሃት ደረጃ እንደሚያሳይ ኢ/ር ይልቃል ገለጹ

$
0
0

9ኙ ፓርቲዎች በትብብር የጠሩትን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በኃይል መበተኑ የስርዓቱ የፍርሃት ደረጃ ጫፍ መድረሱን ያሳያል ሲሉ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
police 3

police 2
police 1
ኢንጅነር ይልቃል በተለይ ሰማያዊ ፓርቲ ከአሁን ቀደም እንደሚያደርገው ለምን እስከመጨረሻው አንበተንም አላላችሁም? ብለን ላቀረብንላቸው ጥያቄ ‹‹የአንድ ወር መርሃ ግብር አውጥተናል፡፡ ምርጫው ነጻና ፍትሓዊ እስኪሆን ድረስ የነጻነት ትግሉ የሚቀጥል ነው፡፡ በአራት ኪሎ አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ጠርተን ልናነጋግር በሞከርንበት ወቅት ብዙ እስርና ደብደባ ተፈጽሟል፡፡ ከዚህ የስርዓቱ ፍርሃት አንጻር ገና በመጀመሪያው ስራችን ወደኃይል እንዲገባ አልፈለግንም፡፡ ለሚቀጥሉት ስራዎቻችን ስንል ነው፡፡ ለሚቀጥለው ያንን በሚመጥን ደረጃ መዘጋጀት አለብን፡፡›› ብለዋል፡፡

ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት አክለውም ‹‹እኛ ዛሬ የአራት ኪሎን አካባቢ ሰዎች ነው የጠራነው፡፡ በዚህ ደረጃ ፈርተው ይህን ስብሰባ ያግዳሉ ብሎ ለመገመት ይከብዳል፡፡ ድሮውንም የሌላቸው የህዝብ ድጋፍ ጭራሹን እንደተሟጠ ነው የሚያሳየው፡፡ ትንሹም ነገር ለስልጣናቸው አስጊ ነው ብለው ማሰባቸው የፍርሃት ደረጃቸው ጫፍ እንደደረሰ ያሳያል፡፡›› ብለዋል፡፡

አዲሱ የአምልኮ፣ አለባበስ እና አመጋገብ ስርዓት በአ. አ. ዩኒቨርሲቲ ከህዳር 30 ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ መመሪያ ተላለፈ

$
0
0

hijab addis ababa
አቡ ዳውድ ኡስማን

ትምህርትህ ሚኒስተር የዜጎችን ህገ መግስታዊ መብት በመጣስ አዲስ ባወጣው የአምልኮ፣ አለባበስ እና አመጋገብ ስርአት ደንብ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከህዳር 30 ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ትዕዛዝ ማስተላለፉን ምንጮች ዘግበዋል፡፡

በአዲሱ የትምህርት ሚኒስተር ደንብ መሰረት ማንም ሙስሊም ሃይማኖቱ የሚደነግግበትን ግዴታዎች መፈፀም የሚከለክል ሲሆን በተለይም ሙስሊም ሴት እህቶቻችን ሂጃባቸውን እንዲያወልቁ አልያ ደግሞ ትምህርታቸውን እንዲያቋርጡ የሚያስገድድ ነው፡፡

ሴኩላሪዝም ሲባል መንግስት እና ሃይማኖት የተለያዩ መሆናቸውን የሚገልፅ መርህ ቢሆንም ሴኩላር ሊሆን የሚችለው መንግስታዊ ስርአቱ እንጂ ሰዎቹ አለመሆናቸው ግልፅ ነው፡፡ ሆኖም ሙስሊሙን ማህበረሰብ ከሃይማኖቱ ለማራቅ ከተነደፈው ዋነኛ ስትራቴጂ አንዱ በትምህርት ቤቶች እና በዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም በመንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ ሙስሊሞች በሃይማኖታቸው ግዴታ የተደረገባቸውን ድንጋጌዎች እንዳይተገብሩ የሚያዝ መመሪያ ማውጣት አንዱ ነው ፡፡

ይህ ህገ ደንብ በረቂቅነት በወጣበት ጊዜ በወቅቱ በሙፍቲህ ሃጂ ኡመር ኢድሪስ በሊቀመንበርነት ይመራ የነበረው የኢትዬጲያ ኡለማዎች ምክር ቤት ህገ ደንቡ ከኢስላማዊ ድንጋጌዎች ጋር የሚጋጭ በመሆኑ ማስተካከያ እንዲደረግበት መጠየቃቸው የሚታወስ ቢሆንም በመንግስታዊ ተሷሚ መጅሊሶች እንዲጸድቅ መደረጉ ይታወቃል፡፡

ይህንንም ህገ ደንብ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተግባራዊ እያደረጉት ሲሆን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም ከ ህዳር 30 ጀምሮ በሁሉም ካምፓስ የሚገኙ አስተዳደሮች እና የጥበቃ ሰራተኞች ህገ ደንቡ ተግባራዊ መሆኑን በጥብቅ እንዲከታተሉ ጥብቅ ማሳሰቢያ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ትዕዛዝ መውጣቱን ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

በመላው ሃገሪቱ ሙስሊም ሴት እህቶቻችን ሂጃባችሁን አውልቁ በሚል ከትምህርት ገበታቸው እየተፈናቀሉ እንደሚገኙ መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡

ቴዲ አፍሮ ለሁለተኛ ጊዜ ዓይኑን በዓይኑ አየ

$
0
0

ቴዲ አፍሮ በፌስቡክ ገጹ ያስተዋወቀን ሁለተኛ ልጁ

ቴዲ አፍሮ በፌስቡክ ገጹ ያስተዋወቀን ሁለተኛ ልጁ


teddy
ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከባለቤቱ አምለሰት ሙጬ ጋር ለሁለተኛ ግዜ አይኑን በአይኑ ማየቱን በትዊተር ገጹ ባሰፈረው የደስታ መግለጫ አስታወቀ::

ቴዲ አፍሮ ከዚህ ቀደም የአንድ ወንድ ልጅ አባት የነበረ ሲሆን ዛሬ ከባለቤቱ አምለሰት ሴት ልጅ ተበርክቶለታል::

“በእግዚአብሔር ፍቃድ ሁለተኛ ልጃችን ይህችን ምድር ተቀላቀለች: : ክብርና ምዝጋና ለመድኃኔዓለም ይሁን!” ያለው ቴዲ አፍሮ ከቤተሰቡ ጋር ለተወሰነ ጊዜ ካሳለፈ በኋላ በሚቀጥለው ወር በአውሮፓ የተለያዩ ከተሞች የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ያቀርባል::
teddy afro tweeter

ቤተክህነትም እንደ ቤተመንግስት የልቡና ድርቅ መቷታል

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live