Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ከወደ ሊባኖስ ዛሬም በሊባኖስ የእኛ አሰቃቂ መከራ ይሰማል …

$
0
0

ነብዩ ሲራክ

ትናንትም ሆነ ዛሬ በሊባኖስ የኢትዮጰውያን የኮንትራት ሰራተኞች ጉዳይ የታዋቂ መገናኛ ብዙሃንና የነዋሪው መነጋገሪያ ከሆነ ቆይቷል ። ትናንት በዋና ከተማዋ በቤሩት በአንድ መኖሪያ መንደር አንዲት ኢትዮጵያዊት ከፎቅ ላይ ተንደርድራ ስትወድቅ የሚያሳየውን ተንቀሳቃሽ ምስል ይዞ የቀረበው ዜና እጅግ አሳዛኝ ነበር ።
Birtukan
መረጃው በአየር ከተለቀቀ በኋላ ጉዳዩን ለማጣራት ባደረግኩት ብርቱካን በሚል ስም የታወቀችው እህት ከሶስተኛ ፎቅ ላይ ስትዘል የወደቀችው ከፎቁ ስር ከነበረ መኪና ላይ በመሆኑ ለመትረፍ መቻሏን ለመረዳት ችያለሁ። ይህችው እህት መካስድ በተባለ ሆስፒታል ICU ላይ ሆና ህክምና አየተሰጣት መሆኑን መረጃዎች ከነምስሉ ደርሶኛል። በጉዳዩ ዙሪያ በሊባኖስ ነጋገርኳቸው ነዋሪዎች ሰቅጣጩን ምስል በዜና እወጃ ሰምተው ማዘናቸውን ገልጸውልኛል። ነዋሪዎች በማከልም ጠንካራ ባለመሆናቸው በሊባኖስ መንግስት በኩል ብዙም ክብር የማይሰጣቸው በሊባኖስ ኢትዮጵያ ቆንስል ሃላፊዎች የወደቀችውን ኢትዮጵያዊት ማንነትና የድርጊቱን መንስኤ ጉዳዩን በቅርብ መከታተል ቢችሉ መልካም ነበር ብለዋል። በአደጋው ዙሪያ ያነጋገርኳቸው ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንስል ባልደረባ በበኩላቸው አደጋ መድረሱ የሰሙት በቴሌቪዥን የሰሙ ሰዎች ወደ ቆንስሉ ለግልጋሎት በመጡ ሰአት በመሆኑን የገለጹልኝ ሲሆን ስለአደጋው ከሊባኖስ መንግስትም ሆነ ከሆስፒታል የደረሳቸው ምነም አይነት መረጃ እንደሌለ ጠቁመውኛል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአንድ ወር በፊት ” ኢትዮጵያውያቷ የቤት ሰራተኛ የአሰሪዎቿን ልጅ አፍና ገደለች ” ብለው በፍርድ ቤት የተያዘውን ጉዳይ ህግን ጥሰው ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል ። ብዙም ሳይቆይ ግን ቀረበው መረጃ ላይ ኢትዮጵያዊቷ በታማኝነት ማገልገሏን ከመሳየት ባለፈ ከሳሽ የሟች አባት ታልታወቀ የክትባት አይነት ከወሰደች በሁለተኛው ቀን የሞተች ልጁን ሬሳ ሳያስመረምር መቅበሩ ፣ ክትባት የሰጠው ጓኛየ ነው ያለውን ዶር ስምና ማንነት ይፋ አላደርግም ማለቱ ጉዳዪን የተገለባበጠ እንዲሆን ማድረጉን ሊባኖሳውያን ሳይቀር ምስክርነት መስጠታቸው አይዘነጋም። ይህም ጉዳይ ለኢትዮጵያዊቷ መብት የሚቆም ቢገኝ ከሳሽን ወደ ተከሳሽነት የሚቀይር ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል ሲነገር በነዋሪው ዘንዳም ሰፊ የመነጋገሪያ ርዕስ ሆኖ ተስተውሎ አደንደነበር ይታወሳል።
እስኪ ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ


የ24 ሰዓት ተቃውሞ በአዲስ አበባ !

$
0
0

ደካማ የመንግስት አስተዳደር ለመለወጥ ምርጫ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም፣ በምርጫ ሥም ጫፍ ላይ የደረሰው ሠላማዊ የነጻነት ትግል ጥያቄ መዳፈን የለበትም፡፡

ይድነቃቸው ከበደ

ይድነቃቸው ከበደ

ይድነቃቸው ከበደ

“ብልህነት የተሞላበት ታላቅ የትግል መርህ ማድረግና መስፋፋት፣ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ፣ጠንካራ ሥራና ሥነ-ሥርዓታዊ አበራታች ትግል ለድል የመብቃቱ ዕድል የሰፋ ነው፡፡” ይህ ፁሑፍ የተወሰደው ከአምባገነን አገዛዝ ወደ ዲሞክራሲ ከሚለው ከ ጄን ሻርፕ መፃሐፍ ነው፡፡ በዙህ አጋጣሚ ይህ መፃፍ እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው፣በተለይ በአገር ውስጥ ለሚንቀሳቁ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ለሚያደርጉት አመፅ አልብ ትግል ብዙ አመላካች መረጃዎችን የሚሰጥ ነው፡፡
ዜጎች በሰላማዊ መንገድ የመሰብሰብና የመንግስትን የፖሊሲ ውሳኔዎች እና አሰራሮች የመቃወም መብታቸው የተጠበቀ ነው፣በሰላማዊ ሰልፍ፣በተቃውሞ የፊርማ ሰነድ ፣ለመንግስት ጥሪ ባለመተባበር፣በሥራ ማቆም አድማና በመሳሰሉት ዘዴዎች ተቃውሞ መግለፅ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የዲሞክራሲ መብት ነው፡፡
addis-ababa-realethiopia-141
በዓለም አቀፍ የተባበሩት መግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ጉባሄ ባፀደቀው መግለጫ ኢትዮጵያም በፈረመችው ስለ መሰብሰብ እና መደራጀት መብቶች የሚከተሉትን ብሏል ‹‹ የዜጎች የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ተግባራዊ ሂደት ገደብ በማይጣልበት ሁኔታ መከበር ሲኖርበት ነገር ግን ገደብ ቢደረግ እንኳን ገደቡ የዓለም ዓቀፍ ህግና ሰብአዊ መብቶችን መሰረት ያደረገ እና የእነዚህን መብቶች ሁለንተናዊ ጥበቃ እዉን የሚያደርግ መሆን አለበት፤በተለይም ዜጎች የፖለቲካ እና የአይማኖት ለማስከበር የሚያደርጓቸው ተቃውሞዎች መደገፍ አለባቸው፡፡ ››የሚል ሲሆን ፡፡የኢፌዴሪ ህገ መንስት አንቀፅ 30 ንዑስ አንቀፅ 1 ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዞ በሰላም የመሰብሰብ ፣ሰላማዊ ሠልፍ የማድረግ ነፃነት እና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ በማለት በህገመንግስቱ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

ሆኖም ግን ይህ መብት ምን ያህል በአገራችን ተፈፃሚ ነው ብሎ መጠየቅ እና ምላሹን ማወቅ ብዙ እርቀት መሄድን የማይጠይቅ አይደለም፡፡ ከዚህ ቀደም በተለያየ ወቅት እና ቦታ በሰማያዊ እና በአንድነት ፓርቲ የተደረጉ አመፅ አልባ የአደባባይ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ምን ያህል ፈተኛ እንደነበሩ ለአብዛኞቻችን ግልፅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ሂደቶ የገዥው መንግስት ፍላጎት ከማስጠበቅ አንፃር እንጂ በየትኛውም ሕግ ድጋፍ ሣይኖረው አብዛኛው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ውጤት አልባ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ይህ ማለት ግን የተደረጉ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ሁሉ ውጤት አልነበራቸውም ማለት አይደለም፡፡ መንግሰት የሕግ ድጋፍ ሣይኖረው በራሱ ፍላጎትና ፍራቻ ብቻ የህዝቡን ቅሬታዎች ሁሉ ጫና በመፍጠር አፍኖን እንገኛለን፡፡

እንዲህ አይነቱን ሕገ-ወጥ መንግስታዊ ሥራ፣ አልቀበለም ማለት የማንኛውም ኢትዮጵያዊ ግዴታም ነው፡፡ይህን ደግሞ የማሳውቅ እና የማንቃት ኃላፊነት ስለ-አገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ሁሉ የሚመለከተው ሲሆን ፣በተለይ ፓርቲዎች የቀን-በቀን ሥራቸው መሆን አለበት፡፡ይሄንን ኃላፊነታቸውን በአግባቡ የተረዱ፣ ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም ትብብር የመሰረቱት ዘጠኝ ፓርቲዎች “ ነፃነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የሕዝባዊ ትግል ፕሮግራም የመጀመሪያ ዙር እንቅስቃሴ ይፋ አድርገዋል፡፡ በኢትዮጵያ የተቃወሞ እንቅስቃሴ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር የተጠራ አመፅ አልባ የ24 ሰዓት የአዳር የአደባባይ የተቃውሞ ትይንት በታሪክ የመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡እንዲህ አይነቱ የሞራል የበላይነት እና ጥልቀት ያለው ሃሳብን የሚጠይቅ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ጥሪ ላስተላለፉት ፓርቲዎች በሙሉ አድናቆትን በሙሉ ልብ የሚያሰጥ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ሌሎች እውነተኛ የተቃዋሚ የፓርቲዎች በትብብሩ ያልታቀፉ፣ በተለይም በሂደቱ ከጅምሩ እስከ መጨረሻው ተሳትፋው በተለያየ ምክንያት የስምምነቱን ሰነድ ያልፈረሙ፣ የተቃውሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ከጋራ ትግሉ ብትቀላቀሉ ውጤቱ የበለጠ ያማረ ይሆናል፡፡በመሆኑም ከሕግ አግባብ ውጪ በማን-አልብኝ እና ትምክተኝነት የተነጠቅነው “የአደባባይ ተቃውሞ” የምናስመልስበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው፡፡

ይዚህ ጽሑፍ አቅራቢ፣ ከዚህ ቀደም “ኢህአዴግ ለምርጫ አልተዘጋጅም” በሚል ርዕስ፡፡ “ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡” ሲል ግንዛቤውን አቅርቧል፡፡

ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ፣ የተዘጋውን በር ለማስከፈት ይቻል ዘንድ በ9 ፓርቲዎች ትብበር ትግሉን የ ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል የፕሮግራም መርህ የመጀመሪያውን ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ የአንድ ወር ዕቅድ አዘጋጅቷል፡፡ በዕቅዳቸው መሠረት ዝግጅቱ የፕሮግራሙ የአፈጻጸም ስልት ፣የጊዜ ሰሌዳ፣ የቦታ ሽፋን፣የፋይናንስ ምንጭ፣ ዓላማዎች፣ትኩረት የሚደረግባቸው ጉዳዮችና መንግስታዊና የህዝብ ክፍሎች፣ዋና ዋና ተግባራት ፣በተጨማሪም በታሳቢነት በአፈጻጸም ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች/ደንቃራዎችና ሥጋቶች እንዲሁም ለፕሮግራሙን ስኬት አጋዥ ሁኔታዎች እንዲካተቱ አድርገዋል፡፡ይህ ደግሞ ከላይ እንደተገለፀው የፓርቲዎቹ ጥንቃቄ የታከለበት ዕቅድ መንደፋቸው የሚያመላክት ነው ፡፡ዘጠኙ የትብብር ፓርቲዎች በህዳር ወር የሚያተኩሩባቸው የተቃወሞ ተግባራትን እንደሚከተለው ይፋ አድረገዋል፡-

1.በየቤተ እምነቱ ጸሎት ፕሮግራም እንዲደረግ ጥሪ ማድረግና አባላት እንደየእምነታቸው ተሳትፎ ማድረግ፤
2. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግ፤
3. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ፤
4. ለመንግሥታዊ ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት፤
5. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት፤
6. የህዝብ ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ፤ ናቸው፡፡

የነዚህ እንቅስቃሴዎች ማጠቃለያ ሕዳር 27 ተጀምሮ ሕዳር 28 የሚያበቃ የ24 ሰዓት የአዳር “የአደባባይ ተቃወሞ” ነው፡፡ በዚህ ፁሑፍ መግቢያ ላይ እንደተገለፀው “ብልህነት የተሞላበት ታላቅ የትግል መርህ ማድረግና መስፋፋት፣ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ፣ጠንካራ ሥራና ሥነ-ሥርዓታዊ አበራታች ትግል ለድል የመብቃቱ ዕድል የሰፋ ነው፡፡” እንደተባለው ሁሉ በዘጠኙ የተቃወሚ ፓርቲዎች የተጠራው የሕዳር ወር የተቃውሞ እንቅስቃሴ በስልት የተሞላ ስለሆነ ሂደቱ እና ውጤቱ ታሪካዊ እንደሚሆን ተስፋ የሚጣልበት ነው፡፡

ገዥው ፓርቲ እንዲህ አይነት ገፍቶ የመጣ ሕዝባዊ ጥያቂ ዕድል በመስጠት ፣ለሚጠየቁ ሕጋዊና ሰላማዊ ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ መስጠት ይጠበቅበታል፡፡ይህ ደግሞ መንግሰት ደግ ስለሆነ የሚያደርገው ሣይሆን ግዴታውም ጭምር ስለሆነ ነው፡፡ሆኖም ግን ከዚህ በተቃራኒ በጦር መሣሪያ ኃይልና በደህንነት አቅም በመመካት የሕዝብን ጥያቄ ለማፈን በተለመደው መልኩ መሄድ ከባድ ቀውሶች እንዲፈጠሩ መመኘት ነው፡፡ ይሁን እንጂ እንዲህ አይነቱ አሉታዊ ነገር መንግስት እንዲፈጠር ቢፈለግ እንኳን፣ ሕዝብ ከፓርቲዎቹ በሚሰጠው መመሪያ ሥነ-ሥርዓታዊና ደፋር እርምጃ ፣ብልህነት የተሞላበት አካሄድ በመከትል ፤አደባባይ ይዞ የወጣውን ጥያቄ ምላሽ አሰጥቶ፣ ሁሉም ነገር በሠላም እንደሚያበቃ የለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ፍላጎት ነው፡፡

በዚህም መሠረት የጉዳዩ ባለቤት የሆኑት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ‹‹የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧል›› ከሚለው አልፎ ‹‹ ተዘግቷል›› ወደሚል ድምዳሜ መሸጋገራቸውን በተጨባጭ ማስረጃ አረጋግጠዋል፡፡እዚህ ደረጃ ላይ መድረሳችሁንም በጋዜጣዊ መግለጫቸው ለሕዝብ አሳውቀዋል፤ሕዝቡ ደግሞ ወትሮም ቢሆን በአገራችን እየተካሄዱ ባሉ ምርጫዎች ሙሉ በሙሉ እምነት የለውም፡፡ይህ ደግሞ “ሰኔ እና ሰኞ” እንደሚባለው ነው፡፡

አሁን ላይ የእምነት ነጻነት ጠያቂዎች፣ጋዜጠኞች፣ጦማሪያን፣የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና አባላት፣ ከገዢው ፓርቲ የተለየ ሃሳብ ያላቸው ዜጎች በአፋኝ ህጎች፣ በፈጠራ ወንጀል ተከሰው አንድም በወህኒ ወይም በስደት ይገኛሉ፡፡በአገራችን የተረጋጋ የፖለቲካ ሥርዓት የለም፣የኑሮ ውድነት የአብዛኛ ኢትዮጵያዊ ትከሻ ያጎበጠ ነው፣ዜጎች በአገራችን ኢትዮጵያ ከቦታ ቦታ ተዘዋውሮ የመንቀሳቀስ እና ንብረት የማፍራት እንዲሁም የመኖር መብት እየተነፈገ ነው፣ሥራ-አጥነት፣ስደት ፣በአገር ላይ ተስፋ መቁረጥ እና ሌሎች መሰል ችግሮች በመንግሰት አስተዳደር ድክመቶች አማካኝነት የተከሰቱ ናቸው፡፡ ስለዚህም እንዲ አይነቱ ደካማ የመንግስት አስተዳደር ለመለወጥ ምርጫ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም፣ በምርጫ ሥም ጫፍ ላይ የደረሰው ሠላማዊ የነጻነት ትግል ጥያቄ መዳፈን የለበትም፡፡

በመጨረሻም ለዚህ ጽሑፍ ማጠቃለይ እንዲሆን ሙሉ በሙሉ ከዘጠኙ የፓርቲዎች ትብብር ከሰጡት ጋዜጣዊ መግላጭ ሃሳብ በመዋስ ነው፣የዚህም ፁሑፍ አቅራቢ ከዚህ የተለይ እምነት የለውምና፡፡

“ ገዢው ፓርቲ በጉዳይ ፈጻሚው የምርጫ ቦርድ በኩል በተለመደው መንገድ በምርጫ ሥም ለመሥራት የተያያዘውን ቧልት ራቁቱን በማስቀረት ለ ነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ፣ የምርጫ ሜዳውን እንዲያስተካክል በሠላማዊ ትግል አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማሳረፍ በእኛ በኩል አስፈላጊውን መስዋዕትነት ሁሉ ለመክፈልና እስከ መጨረሻው በጽናት መቆም ” በማለት ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል ፡፡ይበል !!!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !

ታላቅ ሕዝባዊ የውይይት መድረክ በአምስተርዳም ከተማ * አበራ የማነ አብ * ዶ/ር አረጋዊ በርሔ እና ዶ/ር መላኩ በሚገኙበት

$
0
0

የፊታችን ቅዳሜ ኖቬበር 15 ቀን 2014 ከ 14:00- ጀምሮ
አድራሻ: 1e Helmersstraat 106, 1054 EG Amsterdam next to VENA office
EthioAmsterdam

የማያለቅስ ልጅ –ከዳንኤል ክብረት (ዲ/ን)

$
0
0

daniel-kibret-300x207
ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያንን ሕግ በተመለከተ አሠረ ሐዋርያትን የተከተለ ሆኖ እንዲጸድቅ አድርጓል፡፡ አባቶቻችን በቤተ ክርስቲያን ላይ ግለሰባዊ አምባገነንነትን አልፈቀዱም፡፡ ጸሎተ ሃይማኖቱም ‹ነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት›› በማት ቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ዘሐዋርያት መሆንዋን ያመለክታል፡፡ በ50/51 ዓም በኢየሩሳሌም የተሰበሰበችው ሲኖዶስም ‹እኛና መንፈስ ቅዱስ› አለች እንጂ ‹እኔ› የሚል ግለሰባዊ ድምጽ አልተሰማባትም፡፡
Holy sinod addis ababa
ኢትዮጵያውያን አበው የቅዱስ ሲኖዶስን ሥርዓት ብቻ ሳይሆን ሌሎችን የቤተ ክርስቲያን የአመራር ሥርዓቶች ከግለሰብ አምባገነንነት ለማውጣት መልካም የሆነ ሥርዓት ሠርተዋል፡፡ ቅዳሴው በአምስት ልዑካን እንዲሆን፣ አጥቢያው በሰበካ ጉባኤ እንዲመራ፣ ገዳማት በምርፋቅ (ጉባኤ አበው) ወይም በማኅበር እንዲመሩ፣ ጵጵስናን አንድ ጳጳስ (ፓትርያርክ እንኳን ቢሆን) ብቻውን እንዳይሰጥ፣ ቢያንስ ሦስት አበው ሊኖሩ እንደሚገባ፤ አንድ አባት ብቻውን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንዳይለውጥ፤ አድርገው የሠሩበት አንዱ ምክንያት ግለሰባዊ አምባገነንነትን ለመቋቋም እንዲቻል ነው፡፡

ይህንን ማኅበራዊና ጉባኤያዊ የሆነ የቤተ ክርስቲያን አሠራርና አመራር ለማስወገድ በየዘመናቱ ጥረት ተደርጓል፡፡ የዚህም ምክያቱ ግልጽ ነው፡፡ ግለሰባዊ የሆነ አመራር ለሦስት ነገሮች የተጋለጠ ነውና፡፡ የመጀመሪያው ክህደትንና ኑፋቄን ለማስገባት ይመቻል፡፡ አንዱ ወሳኝ ሌላው ‹ኦሆ በሃሊ› ስለሚሆን እርሱ ትክክል ነው ያለው ትክክል፣ ስሕተት ነው ያለው ደግሞ ስሕተት ይሆናል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ጉባኤያዊት በመሆንዋ አንዳንድ ግለሰቦች በየዘመናቱ ያመጡትን ክህደት በጉባኤ ተመልክታ በጉባኤ ለማውገዝ ጠቅሟታል፡፡ ደገኛ ትምርትና ድርሰት ሲገኝ ደግሞ እንዲሁ በጉባኤ ተመልክታ ለመቀበል ረድቷታል፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ መጽሐፈ ምሥጢርን ጽፎ በጨረሰ ጊዜ ጉባ ሊቃውንቱ ተመልክተው ‹አማንኬ ዮሐንስ አፈወርቅ ወቄርሎስ አፈ በረከት ተንሥኡ በመዋዕሊነ፡፤ ኢትዮጵያ ተመሰለት በቁስጥንጥንያ፤ ወተአረየታ ላዕለ እስክንድርያ – በእውነት ዮሐንስ አፈወርቅና አፈ በረከት የሆነው ቄርሎስ በዘመናችን ተነሥተዋ፡፡ ኢትዮጵያም ቁስጥንጥንያን መስላለች፤ ከእስክንድርያም ልቃ ከፍ ከፍ ብላለች›› ብለው ምስክርነታቸውን ሰጥተው ነበር፡፡

ሁለተኛው ደግሞ ለሌሎች አካላት ቁጥጥር ስለሚመች ነው፡፡ ጌታችን አስቀድሞ ኃይለኛውን ማሠር እንዳለው መሪውን የያዘ ቤተ ክርስቲያኒቱን አን ልቡ ለመዘወር ይመቸዋል፡፡
ይኼ ነገር በዘመነ ሱስንዮስ ጊዜ ታይቷል፡፡ ሮማውያን ግብጻዊውን ጳጳስ በሮማዊ ጳጳስ በመተካት ቤተ ክርስቲያኒቱን በሮማዊ ጳጳስ ለማስመራትና ለመቆጣጠር ፈልገው ነበር፡፡ ነገር ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጠባይ ማኅበራዊና ጉባኤያዊ በመሆኑ ጉባኤ ሊቃውንቱ ከግብጹ ጳጳስ ጋር ሆኖ ተቃወማቸው፡፡ ጳጳሱና ሊቃውንቱም እስከ ደም ማፍሰስ ድረስ መሥዋዕት ሆኑ፡፡ ጥቅምት 19 ቀን 1621 ዓም በምዕራብ ጎጃም በምትገኘው ደብረ መዊዕ የተሰበሰቡት የቤተ ክርስቲያን ማኅበርተኞች ለዚህ ማስረጃ ናቸው፡፡ በዚህ የደብረ መዊዕ ጉባኤ እስከ 7000 የሚደርሱ ምእመናን፣ ካህናት፣ መነኮሳትና ሊቃውንት ተሰባስበው ነበር፡፡ የጉባኤው መሪዎችም እነ አባ ተስፋ ኢየሱስ፣ አባ ዘጊዮርጊስ ዘዋሸራ፣ አባ እንጦንዮስ፣ አባ ግርማ ሥሉስ ዘውይት ነበሩ፡፡ የጉባኤው አፈ ጉባኤ ደግሞ አባ ግርማ ሥሉስ ነበሩ፡፡በዚህ ጉባኤ የተገኙት ሁሉ ንጉሡንና አዲሶቹን ሮማውያን የሃይማኖት መሪዎች ተቃውመው እንደ አንድ ልብ መክረው እንደ አንድ ቃል ተናግረው በተዋሕዶ ጸኑ፡፡ የንጉሥ ሱስንዮስም ጦር ጥቅምት 19 ቀን ከብቦ ፈጃቸው፡፡
እነዚህ ጽኑአን ጉባኤተኞች ነበሩ በኋላ ዐፄ ሱስንዮስ ሐሳባቸውን እንዲቀይሩና ‹ፋሲል ይንገሥ፣ ሃይማኖት ይመለስ› እንዲሉ ያደረጋቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንደ መኪና መሪውን የያዘ መኪናውን ወደ ፈለገው ሊወስደው የሚችልባት ቦታ ብትሆን ኖሮ ዘመነ ሱስንዮስን መሻገር ባልቻለች ነበር፡፡

ሦስተኛው ምክንያት ደግሞ ዘመን የፈቀደለት ሁሉ ልቡ የወደደውን በቤተ ክርስቲያን ላይ እንዳይጭን ነው፡፡ በተለያዩ ዘመናት የተነሡ መንግሥታት ለራሳቸው የሚመቻቸው መሪ በቤተ ክርስቲያን ላይ ለማስቀመጥ ሞክረው ነበር፡፡ የቤተ ከርስቲያን አሠራር፣ ሕግና ሥርዓት ግን በአንድ ሰው የሚዘወር ባለመሆኑ ገመዱን ከመበጣጠስ ያለፈ ጀነሬተሩን ማቋረጥ አልተቻላቸውም፡፡ የቤተ ክርስቲያን ውሳኔዎችም በጉባኤ እንጂ በአንድ ሰው ኅሊና ብቻ የሚወሰኑ ባለመሆናቸው አስተዳደራዊ ጥቅም ከማግኘትና በደል ከማድረስ ባለፈ አጥንቷን ለመስበር ዐቅም አላገኙም፡፡

ይህንን ታሪካዊና ቤተ ክርስቲያናዊ ሐሳብ ጠንቅቆ በመረዳት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ቤተ ክርስቲያኒቱን ወደ ግለሰባዊ አምባገነንነት የሚወስደውን መንገድ በማረም የቤተ ክርስቲያኒቱ ራስ ክርስቶስ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱም የበላይ ወሳኝ አካል ቅዱስ ሲኖዶስ መሆኑን በሕገ ቤተ ክርስቲያን አጽንቶታል፡፡

የሀገራችን ሰው ሲተርት ‹የማያለቅስ ልጅ በእናቱ ጀርባ ይሞታል› ይላል፡፡ ይራበው አይራበው፣ ይታፈን አይታፈን፣ ይመመው አይመመው፣ ይመቸው አይመቸው አይታወቅምና፡፡ ምናልባትም ዝምታው እንደ ጨዋነት ታስቦለት ዘወር ብሎ የሚያየው ላይኖርም ይችላል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በቤተ ክርስቲያን ላይ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ ላይና በሊቃነ ጳጳሳት መብት ላይ፣ ቤተ ክርስቲያንን ሊያገለግሉ በተነሡ ማኅበራትና ወጣቶች ላይ፣ በየገጠሩ በተሠማሩና የመከራ ገፈት በሚቀምሱ ካህናትና ምእመናን ላይ የሚደርሰውን በደልና ጫና እየሰሙና እያዩ ዝም ቢሉ በእናታቸው ጀርባ ላይ ሆነው መሞታቸው የማይቀር ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱን መብት ለማስከበር ደግሞ አስቀድሞ የቅዱስ ሲኖዶሱ መብት መከበር አለበት፡፡ ያልቆመ አንገት ራስን አይሸከምም እንዲሉ፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት አንድ ሆነው የቅዱስ ሲኖዶሱን መብት እንዳስጠበቁትና ቤተ ክርስቲያኒቱንም ከግለሰብ አገዛዝ እንደታደጓት ሁሉ በአጠቃላይ የሰበካ ጉባኤውና በቅዱስ ሲኖዶሱ ጉባኤ የቀረቡትን በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሱ ያሉ ችግሮችን አንድ ሆነው ለመፍታት በቀጣይ መነሣት አለባቸው፡፡

ፓርላማው በሶቨሪን ቦንድ ሽያጭ ላይ በዝግ ተወያየ

$
0
0

ሪፖርተር

parlamaየሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በትላንትናው ውሎው ኢትዮጵያ ‹‹ሶቨሪን ቦንድ›› ለዓለም አቀፍ ገበያ መሸጥ አለበት በሚለው ጉዳይ ላይ በዝግ ተወያይቶ መወሰኑን የሪፖርተር ምንጮች ገለጹ፡፡

ምክር ቤቱ ባካሄደው በዚህ መደበኛ ጉባዔ ላይ አምስት አዋጆች በግልጽ በአጀንዳነት መያዛቸውን የገለጹት ምንጮቻችን፣ የኢትዮጵያና የብራዚል የአቪዬሽን ስምምነትና ሌሎች ተመሳሳይ የሁለትዮሽ ስምምነቶች በይፋ በአጀንዳነት እንደሚታወቁ ገልጸዋል፡፡

በይፋ በአጀንዳነት ያልተያዘውና ለፓርላማ አባላትም ጊዜው እስኪደርስ ያልተነገረው የሶቨሪን ቦንድ ሽያጭ መሆኑን ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠትም በኢኮኖሚ ጉዳዮች ከአገሪቱ ቁልፍ ሰዎች መካከል አንዱ የሆኑት የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር አቶ ሱፊያን አህመድ መገኘታቸውን ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡

በቀረበው አጀንዳ ላይ ፓርላማው ለረዥም ሰዓት ከፍተኛ ክርክር ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ ፓርላማው የተወያየበትን ጉዳይ በዝርዝር እንዲነግሩን የምክር ቤቱ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊን ብንጠይቅም፣ ‹‹በዝግ የተካሄደ ጉዳይ ላይ መረጃ መስጠት አይቻልም፤›› ብለዋል፡፡

ውይይት የተደረገበት አጀንዳ ሶቨሪን ቦንድ ለዓለም ገበያ ማቅረብ የተመለከተ ቢሆንም፣ መረጃው ወደ ውጭ እንዳይወጣ የምክር ቤቱ አባላት እንደተነገራቸውና በጉባዔው ላይ የቀረበው ሰነድም ከፓርላማ እንዳይወጣ የፓርላማው የጽሕፈት ቤት ሠራተኞች ሳይቀሩ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ከምንጮቻችን ለመረዳት ተችሏል፡፡ ጉዳዩን በዝርዝር ለማወቅ ለሚኒስትር ሱፊያን አህመድና የሥራ ባልደረቦቻቸው እንዲሁም አንዳንድ የፓርላማ አባላትን በስልክ የጠየቅን ቢሆንም አልተሳካም፡፡

በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት የኢኮኖሚ ጉዳይ አማካሪና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ በርሄ የሶቨሪን ቦንድ ጉዳይ ለፓርላማ ሊቀርብ የሚችልበት ምክንያትን ከዓለም አቀፍ ልምዳቸው እንዲያስረዱን በጠየቅነው መሠረት፣ ኢትዮጵያ ሶቨሪን ቦንድ ለዓለም አቀፍ ገበያ ማቅረብ አለባት ወይስ የለባትም የሚለውን ተወያይቶ ፓርላማው የማፅደቅ ኃላፊነት ያለበት በመሆኑና ይህንን ኃላፊነትም የትኛው ተቋም ይምራው የሚለውን ለመሰየም ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን ሰጥተዋል፡፡ ጉዳዩ ይህ ከሆነ ኃላፊነቱን በኢትዮጵያ ሁኔታ ሊወሰድ የሚችለው የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ለህዳሴው ግድብ ግንባታ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ቦንድ ሲሸጥ የሚሰጠው የዋስትና ሰርተፍኬት መሆኑን ያስታወሱት ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ፣ ለዓለም አቀፍ ገበያውም የሚሰጠው ሰርተፍኬት ተመሳሳይ ሆኖ አገሪቱ በቦንድ ሸያጩ በውጭ ምንዛሪ የምታገኘውን ብድር የምትከፍለው ዕዳዋ መሆኑን ፓርላማው በሚያፀድቀው አዋጅ ዋስትና መስጠት እንዳለበትም አስረድተዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ዕዳዋን መክፈል አቅቷት ከፍተኛ የብድር ዕዳ ያለባቸው አገሮች ኢኒሼቲቭ (ሂፒኮ) አማካኝነት ከተሰረዘላት በኋላ ስታገኝ የነበረው ብድር ከኮሜርሽያል (ንግድ) ባንኮች ሳይሆን በአገሮች መካከል በሚደረግ መግባባት የረዥም ጊዜ ቀላል ብድር እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ነገር ግን በቅርቡ በኢትዮጵያ መንግሥት የተቀጠሩ ሦስት ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የኢትዮጵያ የውጭ ብድር የመሸከም ጫና ከገመገሙ በኋላ በሰጡት ምዘና ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የቦንድ ገበያ ላይ መሳተፍ እንደምትችል መረጋገጡን ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ ገልጸዋል፡፡

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩም ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የቦንድ ገበያ ውስጥ እንደምትገባና ለዚህም ይረዳ ዘንድ ሦስት ዓለም አቀፍ ኤጀንት (ወካይ) ባንኮችን መመረጣቸውን ባለፈው ጥቅምት ወር መጀመሪያ ላይ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

የሪፖርተር ዝግጅት ክፍል ፓርላማ ስለቀረበው አጀንዳ ማክሰኞ ማምሻውን መረጃ ከማግኘቱ ሰዓታት በፊት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ የሰጡት የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ መንግሥት ከሶቨሪን ቦንድ ሽያጭ ምን ያህል የውጭ ምንዛሪ ብድር ማግኘት እንደሚፈልግ የተጠየቁ ቢሆንም ከመመለስ ተቆጥበዋል፡፡

‹‹ከዓለም አቀፍ የቦንድ ሽያጭ (ሶቨሪን ቦንድ) ምን ያህል ገንዘብ ነው የምንፈልገው የሚለውን የሚመለከተው የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴርን ነው፤›› ብለዋል፡፡

ይሁን እንጂ በጣም ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ በአገር ውስጥ ብር ሊሠሩ የማይችሉና የግድ የውጭ ምንዛሪን የሚጠይቁ የልማት ፕሮጀክቶችን ለመሥራት የሚያስችል ብድር ብቻ በሶቨሪን ቦንድ ሽያጭ ለማግኘት እንደተፈለገ ሚኒስትር ሬድዋን ገልጸዋል፡፡

‹‹እነዚህን ፕሮጀክቶች በመሥራታችንም ኢኮኖሚው ይበልጥ ራሱን መገንባትና የተበደረውንም መክፈል የሚያስችሉ መሆናቸውን ታሳቢ ያደረገ ብድር ለማግኘት እንሠራለን፡፡ ይህም ሲሆን ደግሞ የአገሪቱን የመበደር አቅም ያገናዘበ ኢኮኖሚው በቀላሉ መክፈል የሚችለው መሆን እንዳለበት መንግሥት አምኖ እየሠራ ነው፤›› ብለዋል፡፡

‹‹ከሚፈለገው በታች ብድሩ ቢመጣ መንግሥት የሚፈልገውን ሥራ ለመከወን አያስችለውም፤›› ያሉት አቶ ሬድዋን፣ ‹‹በውጭ ምንዛሪ እጥረት ማነቆ የሚሆንበት ፕሮጀክት የትኛው ነው የሚለው ተለይቶ ለዚያ የሚሆን ገንዘብ ለማምጣት ነው የሶቨሪን ቦንድ ሽያጭ ውስጥ የሚገባው፤›› ብለዋል፡፡

የፕሬዚዳንቱ ልዩ አማካሪ ተነሱ

$
0
0

የፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) ልዩ አማካሪ አቶ አሰፋ ከሲቶ ተነሱ፡፡ አቶ አሰፋ የተነሱት በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ፊርማ በተጻፈ ደብዳቤ ነው፡፡ በአቶ ኃይለ ማርያም ፊርማ የወጣው ደብዳቤ፣ አቶ አሰፋ ከኃላፊነት የተነሱበትን ምክንያት ያልጠቀሰ ሲሆን፣ አቶ አሰፋም በምን ምክንያት እንደተነሱ እንዳላወቁ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

አቶ አሰፋ ከሲቶ

አቶ አሰፋ ከሲቶ

‹‹ወደፊት የሚተገበሩ አዳዲስ ፕሮግራሞችን እየቀረፅኩ ነበር፤›› በማለት ከኃላፊነት መነሳታቸው ያላሰቡትና ያልጠበቁት እንደሆነ አቶ አሰፋ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ደብዳቤው በጥቅሉ፣ አቶ አሰፋ ከኅዳር 2001 ዓ.ም. ጀምሮ የፕሬዚዳንቱ ልዩ አማካሪ በመሆን ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋናውን ገልጿል፡፡

በሥራ አፈጻጸምም ሆነ በሙስና እንዳልተገመገሙ አቶ አሰፋ ለሪፖርተር ገልጸው፣ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር አዲስ የሥራ መደብ እንዲሰጣቸው ደብዳቤ መጻፉን ተናግረዋል፡፡

የሸካ ዞን፣ የኪ ወረዳ፣ የደቡብ ክልል ምክር ቤት ተመራጭ የነበሩት አቶ አሰፋ፣ የክልሉ ፀረ ሙስና ምክትል ኮሚሽነርና የደቡብ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ሠርተዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ለአምስት ዓመታት የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር ሆነው ሠርተዋል፡፡ አቶ አሰፋ የፕሬዚዳንቱ ልዩ አማካሪ ከመሆናቸው በፊት፣ የፍትሕ ሚኒስትር ሆነውም ሠርተዋል፡፡

አቶ አሰፋ የፍትሕ ሚኒስቴርን ለሦስት ዓመታት ከመሩ በኋላ ከቦታው ተነስተው የፕሬዚዳንቱ ልዩ አማካሪ ሆነው ተሰይመዋል፡፡

አቶ አሰፋ ላለፉት ስድስት ዓመታት የቀድሞውን ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስንና በቅርቡ ፕሬዚዳንት ሆነው የተሰየሙትን ዶ/ር ሙላቱ ተሾመን ሲያማክሩ ቆይተዋል፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

የገቢዎችና ጉምሩክ ከፍተኛ ኦፊሰር ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተያዙ

$
0
0

የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ቃሊቲ ጉምሩክ ጽሕፈት ቤት ከፍተኛ ኦፊሰር፣ አቶ ዘመን ይሰማው 40,000 ብር ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል በሚል ተጠርጥረው ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

cuffsየፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በተጠርጣሪው ላይ የመሠረተው ክስ እንደሚያስረዳው፣ የፈረንሣይ ኤምባሲ ሠራተኛ በነበሩት በሚስተር ሚሼል ሪቻርድ ስም የገባ ተሽከርካሪን፣ አቶ ተዋበ ዘለቀ የተባሉ ግለሰብ በ450,000 ብር ይገዛሉ፡፡ ግለሰቡ ተሽከርካሪውን ከገዙ በኋላ የመንግሥት ቀረጥና ታክስ ለመክፈል ወደ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የባለሥልጣኑ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ይሄዳሉ፡፡ የሦስት ዓመታት ግብርና ታክስ 439,586 ብር እንዲከፍሉ ተጠርጣሪው እንደገለጹላቸው ክሱ ያስረዳል፡፡

ግለሰቡም በተጠየቁት መሠረት ክፍያውን ይፈጽማሉ፡፡ ተጠርጣሪው ኦፊሰር ተጨማሪ 146,000 ብር መክፈል እንዳለባቸው ይገልጹላቸውና 60,000 ብር ከሰጧቸው ግን እሳቸው እንደሚጨርሱላቸው ሲገልጹላቸው፣ በሐሳቡ በመስማማት ቅድሚያ ክፍያ 40,000 ብር ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡ ክስ ለመስማት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ለታህሳስ 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ቀጠሮ ይዟል፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

አቃቢ ህግ በጦማርያኑና ጋዜጠኞቹ ላይ የመሰረተውን ክስ እንዲያሻሽል ታዘዘ

$
0
0

•ክሱ ተሻሽሎ መቅረቡን ለማየት ለህዳር 24 ቀጠሮ ተሰጥቷል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

zone9የፌደራል አቃቢ ህግ በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በጦማርያኑና በጋዜጠኞቹ ላይ የመሰረተውን የሽብር ክስ እንዲያሻሽል የልደታ ከፍተኛ ችሎት ትዕዛዝ ሰጠ፡፡
ፍርድ ቤቱ ዛሬ ህዳር 3/2007 ዓ.ም በዋለው ችሎት ቀደም ብሎ የተከሳሽ ጠበቆች ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ መርምሮ ብይን በመስጠት በንባብ አሰምቷል፡፡ በዚህ መሰረትም ፍርድ ቤቱ በክስ መቃወሚያው ላይ የቀረቡትን ዝርዝር ነጥቦች መርምሮ በተወሰኑ ነጥቦች ላይ አቃቢ ህግ ክሱን እንዲያሻሽል ትዕዛዝ ሲሰጥ፣ በሁለተኛነት ቀርቦ የነበረው የክስ ይዘት በአንደኛው የክስ ይዘት ላይ መጠቃለል ስለሚችል ሁለተኛውን የክስ ይዘት ፍርድ ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ አድርጎታል፡፡

በክስ ዝርዝሩ ላይ ተከሳሾቹ ‹‹ለአመጽ ማነሳሳትና መምራት›› የሚያስችል ስልጠና ወስደዋል በሚል በተጠቀሰው ላይ ስልጠናው መቼ፣ በማን እና በምን ጉዳዮች ላይ ተሰጠ የሚለው ግልጽ ስላልሆነ አቃቢ ህግ ክሱን እንዲያሻሽል ተጠይቋል፡፡
በተጨማሪም ተከሳሾቹ አመጽ ለመምራት የስራ ክፍፍል አድርገዋል በሚል የተጠቀሰባቸው የክሱ ይዘት ‹‹ምን አይነት የስራ ክፍፍል፣ ማን ምን እንዲሰራ ክፍፍሉ ተደረገ›› የሚለውን ስለማያመለክት ይህንንም መሻሻል እንዳለበት ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡

በተጨማሪም በክሱ ዝርዝር ላይ ‹‹ቡድን›› እና ‹‹ድርጅት›› በሚል (ግንቦት 7፣ ኦነግ ወይስ ሌላ የሚለውን ስለማይገልጽ) በደፈናው የቀረቡት ነጥቦች ላይ በዝርዝር መቀመጥ ስላለባቸው አቃቢ ህግ ማሻሻያ እንዲያደርግ ታዝዟል፡፡

በሌላ በኩል የተከሳሽ ጠበቆች ‹‹በኢሳት ሬድዮና ቴሌቪዥን መረጃ በመስጠት›› በሚል ተከሳሾች ላይ የቀረበው የክስ ይዘት ሆን ተብሎ ወደ ሌላ አካል (ግንቦት 7) ጋር ለማገናኘት ነው በሚል ያቀረቡትን መቃወሚያ፣ ‹‹በኢሳትና በግንቦት 7 መካከል ያለው ግንኙነት ወደፊት በማስረጃ የሚታይ ነው በሚል ፍርድ ቤቱ መቃወሚያውን ውድቅ አድርጎታል፡፡

ከተከሳሽ ጠበቆች መካከል የሆኑት አቶ አምሃ መኮንን ከችሎቱ በኋላ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት፣ ፍርድ ቤቱ በተከሳሽ ጠበቆች ላይ የቀረበውን የክስ መቃወሚያ ጊዜ ወስዶ መርምሮ ውሳኔ እንዳሳለፈ ጠቅሰዋል፡፡ ይሻሻላሉ የተባሉት የክሱ ይዘቶች ላይ ጥያቄ የተነሳላቸው አቶ አምሃ የውሳኔው ዝርዝር በጽሑፍ ገና እንዳልደረሳቸው ጠቅሰው፣ ‹‹አቃቢ ህግ በታዘዘው መሰረት ክሱን የማያሻሽል ከሆነ ይሻሻላሉ የተባሉት የክሱ ይዘቶች ውድቅ የሚሆኑበት አሰራር አለ›› ብለዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ክሱ ተሻሽሎ መቅረብ አለመቅረቡን ለማየት ለህዳር 24/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡


የቤተክርስቲያንን መፍረስ የተቃወሙት ተደበደቡ

$
0
0

news
ኀዳር ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ 11 በለሚ አካባቢ የምትገኘው ማሪያም ቤተከርስቲያን በህገወጥ መንገድ ተሰርታለች በሚል ፖሊሶች ለማፍረስ ሲሄዱ ህዝቡ ባሰማው ተቃውሞ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ታውቋል።
ድርጊቱን የተቃወሙ ምእመናን “ቤተክርስቲያኑዋን ማፍረስ አትችሉም” ማለት ሲጀምሩ ፖሊሶች መደብደብ የጀመሩ ሲሆን፣ ህዝቡም በአጸፋው በፖሊሶችና በወረዳው አስተዳዳሪ ላይ ድንጋይ በመወርወር የተወሰኑ ፖሊሶችን አቁስሏል። የወረዳው አስተዳዳሪም ጉዳት ደርሶባቸው አምልጠዋል።
ወደ አካበባው በፍጥነት የደረሰው የፌደራል ፖሊስ፣ በቀጥታ የሃይል እርምጃ በመውሰዱ በርካቶች አካላዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል። በስፍራው የነበሩ የአይን እማኞች እንደሚሉት ፌደራል ፖሊሶች በተደጋጋሚ ጥይቶችን ተኩሰዋል። ይሁን እንጅ በብረት ዱላ የምእመኑን እግር በመምታት ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል

ቃለ ምልልስ…. በሊባኖስ ከ4ኛ ፎቅ ከወደቀችው ከእህት ብርቱካን ጋር

$
0
0


ነብዩ ሲራክ ከሳዑዲ አረቢያ

አንዲት እህት ከአራተኛ ፎቅ የመውደቋ መረጃ በሊባኖስ መገናኛ ብዙሃን ሲሰራጭ ከነሰቅጣጭ ተንቀሳቃሽ ምስሉ ነበር ፣ ኢትዮጵያዊቷ እህት ብርቱካን ነበረች ! ለኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ሃገር ቤት የገባችው በአልማዝ ጉዳት ስንቆሰዝምና ” የረጅ የደጋፊ ያለህ !” በማለት እርዳታ ስናሰባስን ከወደ ሊባኖስ ቤሩት በእህት ብርቱካን ላይ ሆኖ አይተነው የሰቀጠጠን ፣ ሰምተነው ያመመን አደጋ ልባችን ሰበረው: (
birtukan
ብዙም ሳይቆይ በብርቱካን ዙሪያ አወዛጋቢ ሪፖርቶች መቅረብ ጀመሩ ፣ እድሜ ለሥነ ቴክኖሎጅ ወሎ አድሮ ነገሩ እየጠራ መጣ ! በሊባኖስ ከሚገኙ ለሰብዕና ባደሩ ቅን ወዳጆቸ ትብበር የብርቱካንን ጉዳይ በቅረብ በመከታየል ብርቱካን ያለችበት ሁኔታ በአንደበቷ እንድታስረዳን ያደረግነው ጥረት ተሳክቷል ! ከብርቱካን በተጨማሪ ጉዳዩ ሚመለከታቸውን ሃላፊዎችና ሃኪሞች በጉዳቷ ዙሪያ አነጋግሬያቸውም ነበር ። የህክምና ባለሙያዎችና በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንስል ሃላፊዎች እንዳሉት ከሆነ ብርቱካን የደረሰባት ጉዳት ለከፋ አደጋ ስላልዳረጋት በቀጣይ ቀናት ከሀኪም ቤት በመውጣትና በተዘጋጀላት ማረፊያ ሆና ህክምናና ጉዳይዋን በፍርድ ቤት እንደምትከታተል ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች ያስረዳሉ ።

ከዚህ በማስከተል በትናንት ሃሙስ ህዳር 3 ቀን 2007 ከቀትር በኋላና አመበሻሹ ላይ እኔ ከሳወዲ ጅዳ ብርቱካንን ከሊባኖስ ቤሩት ሆስፒታል በመሆን በስልክ ያደረግነውን ቃለ ምልልስ ትከታተሉት ዘንድ ግብዣየ ነው !
ቸር ያሰማን

ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 4 ቀን 2007 ዓም

የቴክሳስ ፖሊስ የኢትጵያዊቷ አልማዝ አሟሟት ምክንያት በጥቂቱ ገለጸ

$
0
0

dalas ethiopia

 

 

 

 

 

 

 
almaz
(ዘ-ሐበሻ) የዋይሊ ቴክሳስ ፖሊስ ኢትዮጵያዊቷ አልማዝ ገብረመድህን ከአንድ ወር መጥፋት በኋላ አስከሬኗ መኪናዋ ውስጥ እንዳለች፣ ኩሬ ውስጥ ገብቶ መገኘቱን ተከትሎ የአደጋውን ምክንያት በጥቂቱ ይፋ ማድረጉን አድማስ ራድዮ ከአትላንታ ዘገበ::

አድማስ ራድዮ መርማሪዎቹን ጠቅሶ እንደዘገበው አደጋው የደረሰው በሌላ ጥፋት ወይም በሌላ ኃይል ሳይሆን በተፈጠረ ጥቂት የአነዳድ ስህተት ነው። ኩሬው አካባቢ አሳሳች ምልክት ነበር በዚያ ተሳስታ ወደ ኩሬው ሳትነዳ አልቀረችም ነው የሚለው።

ስምንት ጠቃሚ ነጥቦች ከእስራኤላውያን -ክፍል 2 (ዮፍታሔ)

$
0
0
  1. ድርጅት፣ ድርጅት፣ ድርጅት፤ ተቋማት፣ ተቋማት፣ ተቋማት።

 

Jewish+Ethiopians+Reunited+Families+Israel+o1h5oGhsf2Vlበክፍል አንድ አይሁድ አገራቸውን ከተነጠቁ በኋላ በመላው ዓለም እንደተበተኑ፣ በየሄዱበት አገር ተመሳስለው ለመኖር ቢሞክሩም ከጥቃት እንዳልዳኑ፣ ለዚህ መፍትሔ እንዲሆን ‘አይሁድ ወደ ጽዮን (አገራቸው) ተመልሰው አገራቸውን እንደገና ማቋቋም ያስፈልጋቸዋል’ በማለት ቴዎዶር ሄርዝል (Theodor Herzel) የተባለ የአይሁድ ዝርያ ያለው ጋዜጠኛ ሁሉንም ነፃነት ወዳድ አይሁዳዊ በአንድ ጣራ ሥር የሚያሰባስብ አንድ ጠንካራ ድርጅት በዳያስፖራ ማቋቋሙ ተገልጿል።

በእውነት ድርጅት አገራቸውን በግፍ አገዛዝ ለተነጠቁ ያስመልሳልን? መልሱ ከዚህ ታሪክ በግልጽ እንደምንማረው አዎ! ጠንካራ ድርጅት አገራቸውን በግፈኞች ለተነጠቁ አገራቸውን ያስመልሳል፤ ከአገርም ነፃና የበለጸገች አገር ያጎናጽፋል የሚል ነው። ምን ዓይነት ድርጅት? እንዴት? እኛስ ምን እናድርግ? ይህ ወደመጀመሪያው ትምህርታዊ ነጥብ ይወስደናል።

በእስራኤላውያን (አይሁድ) ላይ የተጋረጠው ችግር ቀላል አልነበረም። ፍልስጤምን (እስራኤልን) የሚያውቀው ትውልድ አልፎ እስራኤልን የማያውቅ ትውልድ ተተክቷል። የእብራይስጥ ቋንቋ እንደመግባቢያ (ንግግር) ቋንቋ ፈጽሞ ጠፍቷል። እንደዛሬው ግዕዝ ሁሉ የእብራይስጥን ቋንቋ ከአምልኮ ስፍራ ውጪ (ከመጽሐፍ በማንበብ ብቻ) ማንም አይገለገልበትም። አሁን ያለው አይሁዳዊ ዝርያ ያለው (አለኝ ብሎ የሚያምነው) ትውልድ በተለያየ አገር የሚኖር፣ ዘሩም፣ ባሕሉም፣ አኗኗሩም እንደየአገሩ የተለያየና ያለበትን አገር ‘አገሬ’ የሚል ነው። በየሚገኝበት አገር ሁሉ ቁጥሩ አናሳና በተናጠል ምንም ዓይነት ተጽእኖ መፍጠር የሚችል አልነበረም። ይህን ሕዝብ በመጀመሪያ ማሰባሰብ ያስፈልጋል።

 

ከዚያም ሞቶ በነበረው አይሁዳዊነት ስሜት ላይ ነፍስ መዝራትና የአንድነትና የመተባበር መንፈስ በዚህ ሕዝብ ውስጥ እንደገና መፍጠር ያስፈልጋል። ያ ከተሳካ በኋላ ደግሞ አይሁድ ተሰባስበው የሚሰፍሩበት ቦታ ያስፈልጋል (የመጀመሪያዎቹ ሰፈራዎች ከፍልስጤማውያን ላይ ቦታ በመግዛት ጭምር የተከናወኑ መሆናቸው ይታወቃል)። ያ ሲሟላ ደግሞ በሚሊዮን የሚቆጠረውን የአይሁድ ዝርያ ያለውን ማኅበረሰብ ከተለያዩ አገራት ወደ እስራኤል ማጓጓዝ ያስፈልጋል። ይህን ለማድረግ አይሁድ ይኖሩባቸው ከነበሩት አገሮች ሁሉ ፈቃድ ያስፈልጋል። ጉዞው በአንድ ጊዜ የተከናወነም ባይሆን ለመጓጓዣ የሚያስፈልገው ገንዘብ ቀላል አልነበረም። በአንድ ጊዜ ብቻ (Fifth Aliyah) ከ 225ሺህ እስከ 300ሺህ ሰዎች የተጓጓዙበት ጊዜ የነበረ ሲሆን በጠቅላላው በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ የአይሁድ ዝርያ ያላቸው ሰዎች ወደ እስራኤል ተጓጉዘዋል።

 

ከዚያም እውቅና ያለው ደኅንነቱ የተረጋጋጠ አገር መመሥረት ያስፈልጋል። ስለፈለጉ አገር መመሥረት ደግሞ በጊዜው ለዚያውም ለአይሁድ ቀላል አልነበረም። በጊዜው ወሳኝ የሆኑትን መንግሥታት (ፍልስጤም ከሮማውያንና ኦቶማን ቱርኮች በኋላ በጊዜው በእንግሊዝ ትተዳደር ነበር) እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶችንና ማኅበረሰቡን ማሳመን ያስፍልግ ነበር።

 

ስለዚህ ችግሩ ቀላል አልነበረም። ቀላል ያልሆነ ችግር ደግሞ ጠንካራ መፍትሔ ያሻዋል። የወርልድ ዛዮኒስት ኦርጋናይዜሽን (World Zionist Organization) ገና ከጅምሩ ሲቋቋም ለዚሁ ታስቦ የተዘጋጀ ጠንካራ ድርጅት ነበር። በየዓለሙ መዳረሻ የአይሁድን ጥቃት ለመከላከል/ለመቋቋም መቻል በራሱ ትልቅ ዓላማ ነበር። ብዙዎች ያሰቡትም ይህ ድርጅት ይህንኑ ሊያደርግ ይችላል የሚል ነበር። ድርጅቱ ግን ይህንንና ሌሎችንም ጠቃሚ ሥራዎች እያደረገ ዋና ግቡን አልፎ ሄዶ እያንዳንዱ አይሁዳዊ በነፃነትና በክብር የሚኖርበት የእኔ የሚለው አገር በመመሥረት ላይ አደረገ። በመጀመሪያ ነገር በየዓለሙ የተበተኑትን አይሁዳውያን በአንድ ማዕከል የሚያሰባስብ የአይሁዳውያን ሁሉ ወኪል የሆነ ዓለም አቀፍ ድርጅት ነበር ማለት ይቻላል። በየአገሩ ተበትነው የነበሩ የአይሁድ ዝርያ ያላቸውን ግለሰቦች አባል እንዲሆኑ ያበረታታል፣ በየአንዳንዱ ከተማ የአይሁድን ቁጥር መዝግቦ ይይዛል፣ ገንዘብና ቁሳቁስ ከአባላቱና ከለጋሽ ግለሰቦች፣ ድርጅቶችና መንግሥታት ያሰባስባል፣ በሥሩ በተለያየ መስክ ሥራ የሚሠሩ ተጨማሪ ተቋማትንና ድርጅቶችን ያቋቁማል፣ በፍልስጤም እና በዳያስፖራ ለሚኖሩ አፋጣኝ ርዳታ ለሚያስፈልጋቸው የገንዘብ፣ የቁሳቁስ፣ የጤናና የትምህርት ርዳታ  ያደርጋል፣ በፍልስጤምና በዳያስፓራ በሚገኙ አይሁድ ላይ የሚቃጣውን ጥቃት ይከላከላል፣ በአይሁዳውያን ዘንድ የግንዛቤ፣ በሌሎች ዘንድ የአይሁዳውያንን ችግር የማስገንዘብ፣ የመቀስቀስና  የፕሮፖጋንዳ ሥራ ይሠራል፣ ከመንግሥታት ጋራ ይገናኛል፣ ተጽእኖ ፈጣሪ ከሆኑ ግለሰቦችና ድርጅቶች ጋራ አብሮ ይሠራል። በአጭሩ ለእስራኤላውያን በውጭ የሚገኝ ጊዜያዊ መንግሥት ነበር ማለት ይቻላል።

 

ለወገኖቹ ለእስራኤላውያን በሠራው ሥራ “የእስራኤል አባት” እየተባለ ሲወደስ የሚኖረው ቴዎዶር ሄርዝል (Theodor Herzel) የዓለም የጽዮናዊነትን ድርጅት ሲያቋቁም ጓደኞቹ ሳይቀሩ እንደ እብድ ቢቆጥሩትም የእርሱ ዓላማ ቆርጦ ለተነሳበት ወገኖቹን የመሰብሰብና አገር የመመሥረት እቅዱ በየደረጃው አስፈላጊ የሆኑትን ዝግጅቶች የሚያሟሉ በሁሉም መስክ ብቃት ያላቸው ጠንካራ ድርጅትና በስሩ በርካታ ተቋማትን መፍጠር ነበር። በዚህም መሠረት በገንዘብ፣ በሰው ኃይልና በእውቀት የዳበሩ ተቋማትን ማቋቋሙን ገፋበት።

 

በሥሩ ካቋቋማቸውና በትብብር ይሠሩ ከነበሩ ጥቂት ድርጅቶችና ተቋማት መካከል “Jewish National Fund/ብሔራዊ የአይሁድ የገንዘብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ” (በፍልስጤም ለአይሁድ መስፈሪያ የሚሆን ቦታ መግዣ ገንዘብ የሚያሰባስብ የነበረ አሁንም ያልከሰመ)፣ የ “Jews Agency/የአይሁድ ወኪል” (ለ3 ሚሊዮን አይሁድ መመለስ ሁኔታዎችን በማመቻቸትና መኖሪያ በማዘጋጀት፣ በአስተዳደር፣ በመረጃ፣ በደኅንነትና በውትድርና በፍልስጤም ድርጅቱን በመወከል ይሠራ የነበረ እስካሁንም ያልከሰመ)፣  “Jewish Federations of North America/የሰሜን አሜሪካ የአይሁድ ፌዴሬሽኖች” (ለ Jews Agency ዋናው የገንዘብ ምንጭ የነበረ፤ በአሜሪካና ካናዳ የሚገኙ በርካታ የአይሁድ ፌዴሬሽኖች በሥሩ ያሰባሰበ ድርጅት)፤ “Zionist Organization of America/የአሜሪካ የጽዮናዊነት ድርጅት” (በአሜሪካ ድርጅቱን በመወከል ዲፕሎማሲን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች እስካሁንም የሚሠራ)፣ “Women’s Zionist Organization of America/የሴቶች ጽዮናዊ ድርጅት በአሜሪካ” (የመጀመሪያዎቹን ነርሶችና ዶክተሮች በውጭ አሰልጥኖ ወደ እስራኤል ከመላክ ጀምሮ በየከተማው ክሊኒኮችን፣ ሆስፒታሎችንና የጤና ምርምር ተቋማትን ያቋቋመ፤ በተጨማሪም የዲፕሎማሲ፣ የማኅበረሰብና የትምህርት ሥራዎችን የሚሠራ ድርጅት)፣ “Women’s International Zionist Organization”/ ዓለማቀፍ የሴቶች ጽዮናዊነት ድርጅት” (በማኅበራዊ ደኅንነት፣ በትምህርትና በሴቶች እኩልነት ላይ ይሠራ የነበረ)፣ “Zionist Youth Movement”/ የወጣቶች ጽዮናዊ ድርጅት (ወጣቶችንና ልጆችን በትምህርት፣ በማኅበራዊና በአይሁድ ባህልና ታሪክ ያሰለጥን የነበረ፤ የትምህርት ፕሮግራሙ በኋላ በእስራኤል የትምህርት ፕሮግራም ተካቷል) እና ሌሎችም ይገኙበታል።

 

እነዚህ ድርጅቶች በሁሉም የተሟሉና ልምድ አስቀድመው ያካበቱ ስለነበረ በ1948 (እ. ኤ. አ) እስራኤል ስትመሠረት የዋናው ድርጅት መሪ ዴቪድ ቤንጉሪዮን (David Ben-Gurion) የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የ “Jews Agency” መሪ የነበረው ቻይም ዋይዝማን (Chaim Wiesmann) የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ለመሆን ሲበቁ በውጭ አስቀድመው የተመሠረቱት በተግባር የተፈተኑት ድርጅቶችና ተቋማት ደግሞ በየመስኩ የአዲሲቱ አገር እስራኤል ተቋማት በመሆን ሊቀጥሉ ችለዋል። በፍልስጤም ለነበሩት ሞዴል በመሆን ያገለገሉትም እነዚሁ በውጭ የተቋቋሙት ድርጅቶችና ተቋማት ነበሩ።

 

ሁላችንንም የሚያሰባስብ እንዲህ ዓይነት ጠንካራ ዓለም አቀፋዊ ድርጅትና በሥሩ የተለያየ ኃላፊነት የሚያከናውኑ ጠንካራ ተቋማት ለእኛ ለኢትዮጵያውያንስ በውጭ አያስፈልጉንም? መልሱ እጅግ በጣም ያስፈልጉናል የሚል ነው። ይህ ቢኖረን ምን ማድረግ እንደምንችል ለመገመት አስቸጋሪ አይደለም።

 

ይህን ለማድረግ የሚያስችሉ አበረታች ጅምሮች አሉን። እነርሱን በማጠናከር ይህን የመሰለ ሥራ የሚሠራ በተለያዩ አገራት የተሰራጨው ሁሉም ነፃነት ወዳድ ኢትዮጵያዊ በአንድ ማዕከል የሚሰባሰብበትና ውጤት የሚያመጣበት በሰው ኃይል፣ በፋይናንስና በእውቀት እጅግ የጠነከረ አሁን ያለንበትን ችግር ማስወገድና ዜጎቿ በነፃነት፣ በእኩልነትና በፍትህ የሚኖሩባት አገር ከማድረግም በላይ በአጭር ጊዜ ከአደጉት አገሮች ተርታ የምትሰለፍ አገር የሚያደርግ ከሁለም የተውጣጣ ድርጅት መመሥረት ይኖርብናል። ይህ የተጋረጠብንን አገር አጥፊ አምባገነንና ዘረኛ አገዛዝ ከማስወገድም በኋላ የሚመሠረተውን ሥርዓት አስተማማኝ ለማድረግ ትልቅ ዋስትና ይኖረዋል።

 

ችግራችን የተወሳሰበ ከመሰለን መፍትሔውም እስካሁን ከሄድንበትና ከተለመደው በተጨማሪ ትንሽ የተለዩና ከዚህ ቀደም በሌሎች ተሞክረው አስተማማኝ ውጤት ያስገኙ መንገዶችንም እንድንከተል ግድ ይለናል።

 

የአገዛዙ ጥቃት ፓለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ ብቻ ሳይሆን ዘርፈ-ብዙ ስለሆነ ትግሉም አንድ አቅጣጫ ብቻ ሳይሆን ዘርፈ ብዙ መሆን ይጠበቅበታል። ስለዚህ በዋናው ድርጅት ጃንጥላ ሥር ራሳቸውን የቻሉ የመረጃ (ጥናትና ምርምር)፣ የቴክኖሎጂ፣ የሕግ፣ የዲፕሎማሲ፣ የትምህርት፣ የጤና፣ የባሕል፣ የቋንቋ ተቋማት መቋቋም ይኖርባቸዋል።

 

ይህን ዋና ድርጅትና ተቋማቱን መመሥረትና ማደራጀት አሁን እየተካሄደ ያለውን የፖለቲካ እንቅስቃሴ በብዙ መቶ እጥፍ ወደፊት እንዲራመድ በማድረግ ድሉን የሚያፋጥንና ከድል በኋላም የሽግግሩንና የአገር ግንባታውን አስተማማኝ የሚያደርግ ቀጣይነት ያለው እንጂ አሁን እየተካሄዱ ባሉት እንቅስቃሴዎች ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያስከትል ተደርጎ መታሰብ አይኖርበትም።

 

ተቃዋሚዎችና ዳያስፖራው ለአገራቸው ምን ሊያደርጉ እንዳሰቡና ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ ከወዲሁ በሥራ የሚያሳዩበትና የሚያስመሰክሩበት እድል ያገኛሉ። የሚሠሩት ሥራና ለሁሉም የሚታየው ድርጅታዊ አቅምና ጉልበታቸው የጠላትን ቅስም የሚሰብር በኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በኃያላኑ መንግሥታት፣ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና በጎረቤት አገራት ዘንድ ከፍተኛ ክብርን፣ መተማመንንና ዋስትናን የሚፈጥር ይሆናል። በአጭሩ አሁን ያለውን ሁኔታ ከመሠረቱ በመገልበጥ (በእንግሊዝኛው Game Changer የሚሉትን ክስተት በመፍጠር) ለአገርና ለመላው ነፃነትና ፍትሕ ወዳድ ሕዝብ አመቺ ሁኔታን የሚፈጥር፣ የሕወኀትን ቀን የሚያሳጥር፣ ሽግግሩን እንከን የለሽ የሚያደርግና መጪውን ጊዜ ሁሉም የሚመኛትን የበለጸገች አገር በአስተማማኝ መገንባት የሚያስችል ያደርገዋል።

 

የዚህን ድርጅት መሥራች ጉባኤ አሁን ካሉት ድርጅቶች የተውጣጣ፣ በሕዝብ አመኔታን ያገኙ የሀይማኖት መሪዎች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ ግለሰቦች የሚገኙበት አካል ለዝግጅት ትንሽ ጊዜ ወስዶ ነገር ግን ሳይውል ሳያድር ለብዙሐኑ አመቺ በሆነ ከተማ ጉባኤውን በተገኘው መንገድ ሁሉ በማሰራጨትና እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዘንድ እንዲደርስ ሰፊ ቅስቀሳ በማድረግ በየመስኩ ያሉትን ባለሙያዎችና መላውን ዳያስፖራ በመጋበዝ፤ በአካል ሊገኝ የማይችለው መላው ኢትዮጵያዊ ከየሚኖርበት ቦታ በቪዲዮ ኮንፈረንስ፣ በስካይፕ (Skype) እና በቀጥታ የሳተላይት ቴሌቪዥን ስርጭት በቀጥታ የሚሳተፍበትንና የሚከታተልበትን የግንኙነት ቴክኖሎጂ አስቀድሞ በማዘጋጀት ይህን መስራች ጉባኤ እውን ሊያደርጉት ይገባል።

 

በዚህ የመጀመሪያውን ነጥብ አጠቃለን ወደሁለተኛው እናልፋለን።

 

  1. የተጋረጠውን ፈተናና መፍትሔውን ዓለምአቀፋዊ ማድረግ።

 

(ይቀጥላል)

 

ኢትዮጵያ በቆራጥ ልጆቿ ሥራ ታፍራና ተከብራ ለዘለዓለም ትኖራለች!

 

 

 

ቃለ ምልልስ (ነቢዩ ሲራክ)

$
0
0

በሊባኖስ ከ4ኛ ፎቅ ከወደቀችው ከእህት ብርቱካን ጋር

    አንዲት እህት ከአራተኛ ፎቅ የመውደቋ መረጃ በሊባኖስ መገናኛ ብዙሃን ሲሰራጭ ከነሰቅጣጭ  ተንቀሳቃሽ ምስሉ ነበር ፣ ኢትዮጵያዊቷ እህት ብርቱካን ነበረች  ! ለኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ሃገር ቤት የገባችው በአልማዝ ጉዳት ስንቆሰዝምና ” የረጅ የደጋፊ ያለህ !” በማለት እርዳታ ስናሰባስን ከወደ ሊባኖስ ቤሩት በእህት ብርቱካን ላይ ሆኖ አይተነው የሰቀጠጠን ፣ ሰምተነው ያመመን አደጋ ልባችን ሰበረው: (

    ብዙም ሳይቆይ በብርቱካን ዙሪያ አወዛጋቢ ሪፖርቶች መቅረብ ጀመሩ ፣ እድሜ ለሥነ ቴክኖሎጅ ወሎ አድሮ ነገሩ እየጠራ መጣ  ! በሊባኖስ ከሚገኙ ለሰብዕና ባደሩ ቅን ወዳጆቸ ትብበር የብርቱካንን ጉዳይ በቅረብ በመከታየል ብርቱካን ያለችበት ሁኔታ በአንደበቷ እንድታስረዳን ያደረግነው ጥረት ተሳክቷል ! ከብርቱካን በተጨማሪ ጉዳዩ ሚመለከታቸውን ሃላፊዎችና ሃኪሞች በጉዳቷ ዙሪያ አነጋግሬያቸውም ነበር ።  የህክምና ባለሙያዎችና በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንስል ሃላፊዎች  እንዳሉት ከሆነ ብርቱካን  የደረሰባት ጉዳት ለከፋ አደጋ ስላልዳረጋት በቀጣይ ቀናት ከሀኪም ቤት በመውጣትና በተዘጋጀላት ማረፊያ ሆና ህክምናና ጉዳይዋን በፍርድ ቤት እንደምትከታተል ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች  ያስረዳሉ ።

ከዚህ በማስከተል በትናንት ሃሙስ ህዳር 3 ቀን 2007 ከቀትር በኋላና አመበሻሹ ላይ እኔ ከሳወዲ ጅዳ ብርቱካንን ከሊባኖስ ቤሩት ሆስፒታል በመሆን በስልክ ያደረግነውን ቃለ ምልልስ ትከታተሉት ዘንድ ግብዣየ ነው  !
ቸር ያሰማን

ህዳር 4 ቀን 2007 ዓም

“የዘረኝነት ስድብ ሲሰድቡኝ እና “ኤቦላ”ሲሉኝ እራሴን ለመከላከል ያደረኩት ነው”- የብሔራዊ ቡድናችን አጥቂ ራምኬል ሎክ ዶንግ በፖሊስ ከተወሰደ በኋላ

$
0
0

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የመብራት ሀይሉ ተስፋ የተጣለበት አጥቂ ራምኬል ሎክ ዶንግ ትላንት በተለያዮ ድህረገፆች ስሙ ከፍርድ ቤት እና በፖሊስ ተይዞ መቅረቡ ተከትሎ በረካታ አስተያየቶች እየተሰጡ ነው።
ramkelኢትዮ-ኪክ ወደ ዋሊያዎቹ ካምፕ ኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል በመደወል ከጋምቤላ ምርጥ ፍሬ እና የዋሊያዎቹ አጥቂ ራምኬል ጋር ያደረገውን ቆይታ እንድታነቡል ብሎም እውነታውን እንድትገነዘቡ ለማድረግ ሞክረናል።
ኢትዮኪክ:- ለቃለምልልሱ ፍቃደኛ በመሆንህ ራምኬሎ ሎክ በአንባባዎቼ ስም እናመስግናለን።
ራምኬሎ:- ኧረ ምንም ችግር የለውም!
ኢትዮኪክ:- ትላንት ምንድነው የተፈጠረው?
አሁንስ ያለኸው የት ነው?
ራምኬሎ:- ጉዳዮ ትላናንት ሳይሆን ከሳምንታት በፊት የፕሪምየር ሊጉን ጨዋታ ከመከላከያ ጋር ከማድረጋችን ከሶስት ቀን በፊት አካባቢ ኤልፖ ካምፖችን በር ላይ ቆሜ የቤተሰብ ጉዳይ እየተነጋገርኩ ሳለ የማላቃቸው ሶስት ሰዎች የዘረኝነት ስድብ እንዲሁም ‘ኤቦላ’ ብለው ሰደቡኝ ከዛ በኃላ ነው ነገሩ የተከሰተው። አሁን ያለሁት ከብሔራዊ ቡድን ጋር ሆቴል።
ኢትዮኪክ:-ጉደዮ የተፈጠረው ቀን ላይ ነው?
ራምኬሎ:- አይደለም ፤ምሽት ለሶስት እሩብ ጉዳይ አካባቢ ነው።
ኢትዮኪክ:- በዛ ሰአት ካምፕ በሩ ላይ ምን እያረክ ነበር?
ራምኬሎ:-ከአንድ ጓደኛዮ ጋር ሹፌር ነው ፤የቤተሰብ ጉዳይ እያዋራውት ነበር። ታናሽ ወንድሜ ታሞ ስለነበር ይሄ ሹፌር በዛኑ ምሽት ወደ ጋንቤላ ስለሚሄድ ለወንድሜ መታከሚያ ገንዘብ ይዞልኝ እንዲሄድ ኤልፖ በር ላይ ቀጥሬው ከእርሱ ጋር እያወራን ባለበት ሰአት ነው ይሄ ነገር የተከሰተው።
ኢትዮኪክ:- ሰዎቹ ስንት ናቸው? ታውቃቸዋለህ?
ራምኬሎ:- እነሱ ሶስት ናቸው። እንደውም አንዱ ከመሀከላቸው የፀጥታ አስከባሪ ልብስ የለበሰ ነው። ሁለቱ መጀመሪያ ‘ኤቦላ ‘ከዛም ዘረኝነት ስድብ ሲሳደቡ አጠገባቸው ያለውን የፀጥታ አስከባሪ ጓደኛቸው የተማመኑ ይመስላል። ከዛ በኃላ ሁለቱ ከእኔ ጋር ድበድብ ጀመሩ አንዱ ደግሞ አብሮኝ የነበረውን ጓደኛዮን ጋር መደባደብ ጀመረ ፣ እነሱ ሶስት ናቸው እኛ ሁለት። በዛ ላይ የፀጥታ አስከባሪ ፀጥታ ማስከበሩን ትቶ ሲሳደቡ እና ሲደባደቡ እኔም እራሴን ለመከላከል ያደረኩት የመልስ ምት ነው።
ኢትዮኪክ:- ምንድነው የደረሰው ጉዳት?
ራምኬሎ:- በድብድቡ ሰአት አንዱ ጥርሱ ወልቄዋለው መሰለኝ፣ አይኑም ሳያብጥ አይቀርም።ሲጀመር እኔ አልደረስኩባቸውም ፣ ሰውም ላይ የምደርስ አይነት ባህሪ የለኝም። እራሳቸው ተሳድበው ሲያበቁ ለመደባደብ ሲመጡ እራሴን ተከላክያለው።
ኢትዮኪክ:- ከእግር ኳስ ውጭ ራምኬሎ ቦክስ ያዘወትራለህ እንዴ?
ራምኬሎ:- [በፈገግታ] ኧሯ ቦክስ እንኳን አላዘወትርም….
ኢትዮኪክ:- ትላንት ፖሊሶች መጥው ሲወስዱህ ደንግጠህ ነበር?
ራምኬሎ:- No! ምንም የሚያስደነግጥ ነገር አልነበረውም።ጉዳዮን ሰምቼ ነበር፤ ከትላንት በስቲያ ሆቴል መጥተው ከቡድን መሪያችን ጋር ተነጋግረው እኔም እሮብ ፍርድ ቤት ቀጠሮ እንዳለኝ ስለተነከገረኝ አልደነገጥኩም። በዛ ላይ እነዚህ የከሰሱኝ ሰዎች ክለቤ በር ላይ ነው የተከሰተው ፤ እኔን መክሰስ ከፈለጉ የት እንደምጫወት ያውቃሉ። እስከዛሬ ቆይተው ብሄራዊ ቡድን ስመረጥ ጠብቀው መክሰሳቸው ሌላ ተልህኮ እንዳላቸው ያሳያል።
ኢትዮኪክ:- እጅህን በሰንሰለት ታስረህ ነበር እንዴ ወደ ህግ ቦታ ስትሄድ?
ራምኬሎ:- ኧሯ የምን ሰንሰለት ፤ እጄን ኬሴ ውስጥ ነበር [ፈገግታ]
ኢትዮኪክ:- አሁን ክሱ በምን ሁኔታ ላይ?
ራምኬሎ:- ከአልጄሪያ ጨዋታ በኃላ እንደገና የፍርድ ቤት ቀጠሮ አለኝ።
ኢትዮኪክ:- እንዴት ነው ይህ ሁኔታ የፈጠረብህ ስሜት ?
ራምኬሎ:- ኧረ ምንም ነገር አልተሰማኝም፤ እኔ ትኩረቴ ብሔራዊ ቡድኑ ነው። ከእኔ የሚፈለገውን ማደረግ ነው ለብሔራዊ ቡድናችን ማገልገል።
ኢትዮኪክ:- ዛሬ ምሽት ወደ አልጄሪያ ትጓዛላችሁ ፤ ራምኬሎ በአልጄሪያ ጨዋታ ምን ያስባል?
ራምኬሎ:- እኔ እንግድህ ብሔራዊ ቡድኑ ከተጠራው ጀምሮ ሀሳቤ አንድ ነው፤ በተቻለኝ አቅም ብሔራዊ ቡድናችን የአልጄሪያ ጨዋታ አሸንፈን መምጣት ነው የማስብው።
ኢትዮኪክ:- ስለነበረን ቆይታ ራምኬሎን ከልብ አድርገን እናመሰግናል።

ምንጭ: ኢትዮኪክ

ቤተክርስቲያን እንዳይፈርስ የተቃወሙት ዜጎች ታፍሰው የት እንደደረሱ አልታወቀም; “ይህ ሁሉ የሆነው የእምነቱን ተከታዮች በመናቅ ነው”

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) ትናንት ህዳር 3/2007 ዓ.ም ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ የማሪያም ቤተ ክርስቲያን እንዳይፈርስ በመቃወማቸው የታፈኑት ዜጎች የት እንደደረሱ አልታወቀም ሲሉ በወቅቱ ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩ የአካባቢው ነዋሪዎችና የእምነቱ ተከታዮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
news
በወቅቱ 600 ያህል ዜጎች ተገኝተው ቤተ ክርስቲያኗ እንዳትፈርስ ሲቃወሙ እንደተመለከቱ የገለጹት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች የቤተ ክርስቲያኗን መፍረስ የተቃወሙትን ጨምሮ ሌሎች በአካባቢው የተገኙ ዜጎችም በፖሊስ መታፈሳቸውን ገልጸዋል፡፡ ነዋሪዎቹ ‹‹ህዝቡ በሰንደቅ አላማ አምላክ አታፍርሱብን እያለ ቢለምንም እነሱ ግን ጥይት ወደላይ በመተኩስ ህዝቡን ከማሸበራቸውም በላይ ያገኙትን እየደበደቡ በ9 የድንጋይ መጫኛ መኪና አስገድደው በመጫን ወዳልታወቀ ቦታ ውስደዋቸዋል፡፡ አድማ በታኝ ፖሊስ ቄስ፣ አዛውንት፣ ህጻንና ሴት ሳይል ያገኘውም አፍሶ ወስዷል፡፡ የኮብል ስቶን ጠራቢዎች ሳይቀሩ በአካባቢው በመገኘታቸው ታፍሰው ታስረዋል፡፡ አሁን የት እንዳሉ አይታወቅም፡፡›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ቤተ ክርስቲያኗ ከተሰራች ከሁለት አመት በላይ እንደሆነ የገለጹት አንድ የአካባቢው ነዋሪ ‹‹ቤተ ክርስቲያኗ ከተሰራችበት ጊዜ ጀምሮ እንድትፈርስ ጥያቄ እንደቀረበ ተገልጾልን አያውውም፡፡ አሁን ነው ደርሰው ያፈረሱት፡፡ የቤተ ክርስቲያኗን አገልጋዮች ጨምሮ በጣም ብዙ ሰው በዱላ ተደብድቧል፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው የእምነቱን ተከታዮች በመናቅ ነው፡፡›› ሲሉ ቅሬታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎችና አማኞች ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ እስከ 9 ሰዓት ቤተ ክርስትያኗ እንዳትፈርስ እንደተቃወሙ፣ አድማ በታኝ ፖሊስ በአካባቢው ያገኘውን ሰው ካፈሰ በኋላ ቤተ ክርስቲያኗን በማፍረስ ቆርቆሮውን በመኪና ጭኖ እንደሄደ የአይን እማኞች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡


ልማታዊው ጭፍጨፋ በአፋር ክልል በ ግንቦት 2003 ዓ.ም

$
0
0

አኩ ኢብን አፋር

ምን ጊዜውም በአፋር ህዝብ ዘንድ የማይረሳ ቀን ነው!!
የተፈጸመው በአፋር ክልል በዱብቲ ወረዳ ነው።

police afar
በ2003 ዓ.ም አንድ አሊ ኡመር የተባለ የ10ኛ ክፊል ተማሪ የሆነው ወጣት ሌሊት በሱኳር ፋብሪካ ዘበኛ ሁኖ ሰለሚስራ ጧት ደግሞ የጦር መሰራውን እቤት አስቀምጦ ወደ ትምህርት ቤቱ የሄዳል።
እንደተለመደው ተማሪ አሊ ኡመር ከአንድ ጓደኛው ጋር የጦር መሳሪያውን ይዞ ከተኛበት የስራ ቦታ ወደ ቤቱ በመሄድ ላይ ሳለ ሁለት የፈደራል ፖሊሶች በመንገድ ላይ ያገኙዋቸዋል። መሳሪያውን አስረክብ አሉት!

ልጁ ደግሞ ማንነቱን በሚገባ ካስረዳቸው በኃላ መሳሪያውን ህጋዊ መሆኑንና እሱ በሱኳር ፋብሪካ ዘበኛ እንደሆነ ነገራቸው።

አሁንም መሳሪያውን አስረክብ አሉት እሱም እኔም ህጋዊ ዘበኛ ነኝ መሳሪዬም ህጋዊ ነው እንጂ አላሰረከብም አላቸው።

ከዛ ከፖሊሶቹ አንደኛው ለምን ብዙ ትከራከረዋለህ በማለት ጭንቅላቱን መቶ ገደለው አብሮት የነበረው ልጅም ወሰዱት እየደበደቡት ከዋሉ በኃላ ማታ ለቀቁት።
ይሁን እንጅ ችግሩ ተባብሶ ቀጠለ። የማቹ ቤተሰቦች ፖሊሱን ለህግ እንድቀርብ ደጋግሞው ቢጠይቁም ሰሚ አላገኙም።
ሁለት የማቹ ቤተሰብ የሆኑት ወጣቶች ልጁን ገድሎ ለህግ ያልቀረበ ፖሊሱን ፈለገው ገደሉት እነዚህ ሁለት ወጣቶች በጊዜው በአፋር ክልላዊ ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ወንጃለቻው ተጣርቶ ለፊርድ ቤት መቅረብ የነበረባቸው ቢሆንም በአቶ እስማእል አሊ ሲሮ የስልክ ትዕዛዝ መሰረት በሚሌ ካንፖ ለሚገኘው ፈደራል ፖሊስ አሳልፈው ሰጡዋቸው ፈዳራል ፖሊስም እነዚህ ወጣቶች ልክ ሚሌ እንደወሰዷቸው ገደሉዋቸው።
ይህን ተከትሎ የማቹ ጎሳ መሪን ጨምሮ ቤተሰቦቹ ሁሉም ታሰሩ።
ያለ ፊርድ ለ3 አመታት በሚሌ በፈደራል ፖሊሶች ከተሰቃዩ በኃላ ባለፉት ሦስት ወራት ውስጥ ተለቀዋል ከነዚህ ውስጥ በመጀመሪያ በፖሊስ የተገደለው አሊ ኡመር ወንድም አለ።

እነርሱም
1 ናስሪ አሊ ሀማድ
2 ሓቴ ዑመር ( የማቹ ወንድም )
3 ዳውድ ዑማር
4 ካዲር አስከር
5 አሊ ሓማድ ስሆኑ ከ3 አመታት በላይ በደብደባ፣ሙቀት፣ በረሃብ አንዲሁም በውኃ ጥም እያሰቃዩዋቸው እንደነበሩ ለምንጮችን ተናገሯል።
አሁንም ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ እስር ላይ የሚገኙ እንዳሉ ተጠቀመዋል።
1 ዑመር የተባለ ለጊዜው የአባቱ ስም አልታወቀም
2 አሊ ሩዔ
3 መሐመድ ማያባሄ እነዚህ ግለሰቦች እስካሁን በግፍ ታስረው በመሰቃየት ላይ መሆናቸው ተገልፇል።
ባለፈው ሳምንት በሰመራ ከተማ የፅጥታ ጉዳይን በተመለከተ ስብሰባ እንደነበረና አብዴፓዎች ስለዚህ ጉዳይ ከምረጫ በፊት በፍታ ቤሄር እንድጨርሱ ከህወሀት ትዕዛዝ መተላለፉን የሰመራ ምንጮች ለአኩ ኢብን አፋር ዘግቧል።

አቶ ማሙሸት አማረ :- አዲሱ የመኢአድ ፕሬዝዳንት ተስፋና ተግዳሮት

$
0
0

“የቱ ይቀድማል?:-

aeupበዲክራሲያዊ መርህ ላይ የቆመ ሀገር ወይስ ዲሞክራሲን ሊሸከም የሚችል ባህል ላይ የቆመ ማህበረሰብ ?” በሚለዉ ጽሁፌ
የፖለቲካ ፓርቲዎቻችን የዉይይትና የክርክር ባህል አለመዳበርን በማስመልከት የተወሰኑ ፓርቲዎችን እያነሳሁ ወቅሼአቸዉ ነበር:: ፓርቲዎች ዉስጥ በግለሰብ ወይም በቡድን ደረጃ የሀሳብ ክፍፍል ሲነሳ ፓርቲዎች በሀሳብ የመሸናነፍ ባህል እንዳላዳበሩ ምሳሌ አድርጌ ካቀረብኩት ፓርቲ አንዱ የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ነበር:: እንዲህም ስል ፓርቲዉን በሀሳብ ሸንቆጥ አድርጌዉ ነበር:-

[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

አለማወቅ እንደልብ ያደርጋል! ማተብ እንቆርጣለን ያሰኛል! (ተክሌ የሻው)

$
0
0

ተክሌ የሻው
አለማወቅ እንደልብ ያናግራል። አላዋቂ ሰዎች ሲገሩ ካፋቸው የሚወጣው ቃል በማኅበረሰቡ ባህል፣ ወግ፣ አኗኗር፣ ሰላምና አጠቃላይ ማኅበራዊ ግንኙነት ውስጥ ሊያስከትል የሚችለውን ጥቅምና ጉዳት አያመዛዝኑም። ከአንደበታቸው የሚወጣው ቃል በትውልድ ላይ ጥሎት ሊያልፍ የሚችለውን መጥፎም ሆነ መልካም አሻራ አይመዝኑም። በመሆኑም ንግግራቸው አንደበታቸው ያቀበላቸውን እንደወረደ ወደ አድማጫቸው ስለሚለቁት የሰዎችን አዕምሮ ያቆስላል፤ የማኅበረሰቡን ባሕልና ወግ ይንዳል። ከሁሉም በላይ አላዋቂነት በፖለቲካ ሥልጣን ሲታጀብ ማን አህሎኝነት ስለሚጨመርበት የሚናገሩት ንግግር ልጓም አልባ ስለሚሆን ንግግራቸው ከጥቅሙ ጉዳቱ በእጅጉ ይበላጣል። ይህም ለአገርና ለትውልድ የነገር፣ የቂምና የጥላቻን ቁርሾ ጥሎ ስለሚያልፍ የሰላምና የአንድነት ፀር ይሆናል። ባጭር አገላለጽ « አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል» ዓይነት ነው።

ለዚህ አባባል ሰሞኑን የኢትዮጵያው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ነኝ የሚለው ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም የተባለው ማተብን አስመልክቶ የተናገረው ጥሩ ያላዋቂነት ምሳሌ ነው። ሰውየው «ማተብ የክርስትና ሃይማኖት መለያና ምልክት ከሆነ እንቆርጣለን» ሲል፣አፉን ሞልቶ በማን አለብኝነት የተናገረው ፣«ጨዋታ ሲደራ እናቴ ባርያ ናት» ያሰኛል እንደሚባለው፣አባባሉ ሊያስከትል የሚችለውን ሁኔታ፣ በማኅበረሰቡ አጠቃላይ ግንኙነት ሊፈጥር የሚችለውን እንደምታ አለማወቅ ወይም ማመዛዘን አለመቻል የወለደው እብሪት እና ድንቁርና ነው።

በአንፃሩ ዐዋቂዎች የሚናገሩትን በማስረጃ ስለሚያስደግፉ የሰሚዎቻቸውን አዕምሮ እና ኅሊና ይስባሉ። አድማጫቸውን ያስደስታሉ፣ ያሳውቃሉ፣ ያዝናናሉ። የዘሩት መብቀል ብቻ ሳይሆን ያፈራል ። ሰዎችን አያስከፉም፤ የሌሎችን መብት አይፃረሩም፤ የማኅበረሰቡን ባሕልና ወግ ያከብራሉ፤ ይጠብቃሉ፤ የነርሱን መልካም ነገር በመጨመር ያለፈውን በመልካም ጎኑ እንዲዳብር ያደርጋሉ። የንንግግራቸው መቋጫ አንድነትና ሰላም ነው።

እንዳው ወደማተብ ቆረጣው ይሳካል፣ አይሳካም፣ ወደሚለው ከመግባታችን በፊት የማተብን ምንነት፣ በኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ውስጥ ያለውን ባሕላዊ፣ ሃይማኖታዊ ፋይዳና የያዘውን ዕሴት እንመልከት።

በኢትዮጵያውያን የቆየ መልካም ባሕል ውስጥ ማተብ ልዩ ቦታና ትርጉም ያለው የሐቅና የዕውነት ማስረገጫ፣ የተገቢና የትክክለኛ ነገር መግለጫ ነው። አዋ እገሌ፣ እሜቴ እገሊት ማተበ ጥኑ ናቸው፤ አቶ እገሌ፣ ወ/ሮ እገሊት ባለማተብ ናቸው፤ የሚባሉት አባባሎች አደራ ተቀባዮችን፣አደራ አስቀማጮችንና የታማኝ ሰዎችን ሥብዕና የሚንገልጽበት ኃይለ ቃል ነው። « የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፍ» ብለው ለቃላቸው የሚቆሙትን፣ ሃይማኖት አክባሪ፣ እግዚአብሔን ፈሪ የሆኑ ሰዎችን ከሌሎቹ ለይተን የምንጠራበት ውብ የሐቅ መገለጫ ቃል ነው። ቃሉ የራሳቸውን ለመለገስ እንጂ፣የሌሎችን ቤሳ ቤስቲ የማይፈልጉትን፣ አጠቃላይ ሕይዎታቸውና ኑሮአቸው ሐቅን፤ ዕውነትን መሠረት አድርገው የሚንቀሳቀሱ ሰዎች ማንነት መገላጫ የሆነ ቃል ነው። ይህ ቃል ከቃልነት አልፎ የሐቅ መገለጫ ለመሆን የበቃ ስለሆነ ባህል ነው። የዕውነት መገለጫ ነው።

በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ ማተብ የሥላሴዎች አንድነትና ሦስትነት የሚገለጽበት ረቂቅ ሚስጥር የያዘ ነው። በማቲዎስ ወንጌል ምዕራፍ 28 ከቁጥር 18 እስከ 20 እንዲህ ይላል። « ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፣ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፣ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆ እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተጋር ነኝ።» ሲል አምላካችንና ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሠረት የሚፈጸም ተጠማቂው ከመንፈስ ቅዱስ የመወለዱ ምልክት ነው። አጥማቂው ካህን «በአብ ስም አጠምቅሃለሁ፤ በወልድ ስም አጠምቅሃለሁ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠምቅሃለሁ፤» ካለ በኋላ ለመጠመቁ ምልክት ይሆን ዘንድ ፣ሦስት ጥቁር፣ቀይና ብጫ ቀለም ያላቸውን ክሮችን ባንድነት ገምደው (ሸርበው) በአንገቱ ላይ ያስራሉ። የክሮቹ ሦስትነት የአብ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ሲሆን፣ ተገምደው አንድ መሆናቸው የሥላሶችን ሦስትነትና አንድነት ምሳሌ ነው።

የቀለሞቹ ትርጉምም ቀዩ የሰማዕትነት፣ ጥቁሩ መሰቀሉንና መከራ የመቀበሉ፣ብጫው የመንግሥተ ሰማየት ተስፋ ምልክቶች ናቸው። ጥምቀት ወንድ በተወለደ በ40 ቀኑ፣ ሴት በ80 ቀኗ የሚከናወን ፣ተጠማቂዎቹ ከመንፈስ ቅዱስ የመወለዳቸው መረጋገጫ ነው። ሁለት ልደት የምንለውም ሰው በአካል ከወላጆቹ የመወለዱ አንዱ ሲሆን፣ሁለተኛው በመጠመቁ ከመንፈስ ቅዱስ የመወለዱ ሚስጢር ነው።

ማንም የኢትዮጵያን ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ሃይማኖት ቀኖና፣ዶግማ፣ ሥርዓትና ታሪክ ጠንቅቆ ለሚያውቅ ሰው የመጀመሪያዋ ብቸኛ የመንግሥትና የሕዝብ ሃይማኖት ሆና በአብርሃና በአጽብሃ ዘመን የታወጀች ሃይማኖት መሆኗን አይዘነጋም። ቤተክርስቲያኒቱ በዚህ ዕድሜ ጠገብ በሆነ ረጅም ታሪኳ ለኢትዮጵያና ለዓለም ሕዝብ እጅግ ብርቅና ድንቅ የሆኑ ዘመን የማይሽራቸው የቋንቋ፣ የሥዕል፣ የሥነ ሕንፃ፣ የመድኃኒት ቅመማ፣ የሥነፍጥረት፣ የቀን አቆጣጠር ቀመርን ያበረከተች ናት። ዛሬ የአገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ማፍሪያ ከሆኑት አንዱ የሆነው የቱሪስት መስኅቦች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ውጤቶች ናቸው። የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያኖች፣ ጣና ሐይቅ ውስጥ የሚገኙ አድባራትና ገዳማት፣ መሰቅል (ደመራ)፣ ጥምቀት፣ የያሬድ ዝማሬና መሰሎቹ የቤተክርስቲያኑቱ አንጡራ ሀብቶች ናቸው።

ለግዕዝና ለአማርኛ ቋንቋ ድምፅ የሚወክሉ ፊደሎችን ከነሥርዓታቸው ቀርጻው ቋንቋውን የቃል ብቻ ሳይሆን፣ በጽሑፍም እንዲገለጽ ያደረገች ናት። ሌጦን ፍቀውና አለስልሰው ብራና ሠርተው መጽሐፍን ደጉሰው ታሪክ ለትውልድ እንዲተላለፍ ያደረገች ናት። ከመቃ ብዕር ሠርታ ጽሕፈትን ያስተማረች ናት። ሊቃውንቶቿ፣ሥራሥሩን ምሰው፣ ቅጠላቅጠሉን በጥሰው ቀጥቅጠውና ጨምቀው የሠሩት ቀለም እስካሁን በውበቱም ሆነ በጥራቱ ተወዳዳሪ ያልተገኘለትን ቀለም ያበረከተች ናት። ይህም በመሆኑ የሃይማኖቷ ሥርዓት ከሃይማኖትነት አልፎ የሕዝቡ ባሕልና የኢትዮጵያዊነት መልካም መታወቂ ለመሆን የበቃ ነው።

ቤተክርስቲያኗ እንደዛሬው ሕዝቡ ወንጀለኞችን የሚዳኝበት የወንጀለኛ መቅጫ እና የፍትሐብሔር ሕግ ሳይኖር፣ ፍትሐ-ነገሥትን ከዓለማዊና ከመንፈሣዊ ሕይዎት ጋር አጣጥማ ሕዝቡ ፍትሕን እንዲያገኝ የሕግን ሥርዓት በተጨባጭ ያሳየችና ያስተማረች ናት።

በሌላ በኩል የኦርቶዶክስ ሃይማኖት «አትግደል፣ አታመንዝር፤ አትስረቅ፣ አትዋሽ፣ በውሸት አትመስክር ፣ወዘተ» የሚለውን አምላካዊ ቃል አጥብቃ ስለምትከተል አማኟ ሰብአዊነትን፣ ሕጋዊነትን፣ ሰው አክባሪነትን፣ ሐቀኝነትን፣ ባህሉ እንዲሆን( ይህ ዘመናዊነት የተባለው አመለካከት ገብቶ ክሕደትና ቅጥፈት በአገሪቱ ሕዝብ ሥነልቦና ውስጥ ሁነኛ ቦታ እስኪይዝ ) ከፍተኛ ሚና የተጫዎተች ናት። ሕዝቡ መልካሙንና መጥፎውን፣ ደጉንና ክፉውን፣ ዓለማዊውንና መንፈሣዊውን ለይቶ እንዲያውቅ ያስተማረች ወንጌልን የሰበከችና ያስፋፋች በመሆኗ የአገርና የሕዝብ ባለውለታ ናት። ይህም ብቻ አይደለም፤ አገርን የሚወር፣ ሃይማኖትን የሚያስክድ፣ ነፃነትን የሚገፍ፣ ወራሪ ኃይል ሲነሣ፣ ሕዝቡን አስተባብራ በወራሪዎች ላይ ክንዱን በማንሳት ነፃነቱን እንዲጠብቅ፣ ሃይማኖቱን እንዲያጠና፣ የአገሩን አንድነት እንዲያስከብር የግንባር ቀደምትነት ሚና ስትጫዎት የኖረች ናት፤ ፍትሕ ሲጓደል፣ድሐ ሲበደል ነገሥታቱን የምትገስጽ፣ እንዲያም ሲል እንደዛሬው ሳይሆን፣ሕዝቡን አስተባብራ በክፉዎችና ባረመኔዎች ላይ የምታስነሳ የፍትሕ ተቋም ናት።

ይህን ሁሉ አጣምረን ስናይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋህዶ ሃይማኖት ከእምነት አልፎ ባሕልና የመልካም ሥርዓት መሠረት ለመሆን የበቃ ነው። የሃይማኖቱ ሥርዓት እንግዳ መቀበልና ማክበርን፣ ባይተዋርን መርዳትና መንከባከብን፣ ለተራቡ መመገብን፣ ለታረዙ ማልበስን ለተጠሙ ማጠጣትን፣ ለታሰሩ ማስፈታትን የጽድቅና የመልካም ሥራ አርኣያ አድርጎ ስለሚወስድ የተለያዩ ሃይማኖቶች ወደ አገሪቱ ሲገቡ የተቃውሞ ድምፅ አልተሰማም። ለዚህም ነው የነበዩ መሐመድ ቤተሰቦች በቁራይሾች ሲሳደዱ፣ ነቢዩ «ወደ ኢትዮጵያ ሂዱ፣ከዚያ መልካም የክርስቲያን መንግሥት አለ» ብለው የላኩዋቸውና ከጥፋት ለመዳን የበቁት። ለዚህም ነቢዩ መሐመድ ባለማተብ (ሀቀኛ) ስለነበሩ፣ውለታን አዋቂ በመሆናቸው ማነኛውም የእስልምና ተከታይ ኢትዮጵያን እንዳይነካ ነቢያዊ ቃል የሰጡት። እስልምናም ሆነ ሌሎች ሃይማኖቶች በአገሪቱ ውስጥ በእንግድነት ሲገቡ ፣የአገሪቱና የሕዝቡ ሃይማኖት የሆነው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት በማናቸውም ሃይማኖት ላይ ጥላቻ ሳያሳድር ጎን ለጎን መኖር የተቻለው፤ሃይማኖቱ እንግዳ ተቀባይ፣ የተቸገረ ረጅ፣ ላጣ መጽዋች ከመሆኑ የመነጨ ነው። ዕውነተኛው ታሪክ ይህ መሆኑ በግልጽ እየታየና እየታወቀ፣ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ተጽዕኖ ደርሶብናል፣ በአክራሪ ኦርቶዶክሶች ተበድለናል የሚሉ ወገኖች ፣ዛሬ ከሃይማኖት አልፎ የሕዝቡና የኢትዮጵያዊነት መታወቂያ፣ የሐቅ መግለጫ የሆነውን ማተብ እንቆርጣለን ሲሉ መደመጣቸው በማተቡና በሕዝቡ ባሕል፣ በማተቡና በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት መካከል ያለውን ቁርኝትና አንድነት በቅጡ ካለማወቅ ወይም «ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ ጅግራናት ይሏታል» እንዲሉ፣ በዚህ አመካኝተው ይህኑ ከኦርቶዶክስ ሃይማኖት ጋር ቁርኝት አለው የሚባለውን የዐማራ ነገድ ነጥሎ ለመምታት የተሸረበ ታላቅ ሤራ መኖሩን የሚጠቁም እንደሆነ መገንዘብ አይገድም።

ሕዝቡ፣ በተለይም የኦርቶዶክስ ሃማኖት አማኙ፣ ማወቅ ያለበት፣ ባንዲራ ያንዲት አገር መለያ፣ መታወቂ እንደሆነ ሁሉ፣ ማተብም የኦርቶቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ መለያ፣ ከመንፈስ ቅዱስ ስለመወለድ ማረጋገጫ የሆነ ነው። ማተብ ካንገት መበጠስ የሚቻለው ኦርቶዶክሳውያንን በፍፁም ማጥፋት ሲቻል ብቻ ነው። ይህ እንዳይሆን ኦርቶዶክሳውያን ሃይማኖታዊ ሥርዓታቸው በሚያዘው መሠረት ሃይማኖተ ጥኑ፣ ለዕውነት ሟችና ተሟጋች ሆነው መቆም ይጠበቅባቸዋል።

ሌላው መታወቅ ያለበት የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ሰው አከረረ ወይም አክራሪ ነው የሚባለው፣ ይህን ዓለም ትቶ፣ለማያልፈውና ለወዲያኛው ዓለም ቤቱን ለመሥራት በፀሎትና በስግደት ተወስኖ ለመኖር ገዳም ሲገባነው። ሃይማኖቱ አትግደል ስለሚል፣መግደል ታላቅ ሐጢያት በመሆኑ፣ ክርስቲያን በመግደል አክራሪ ሊሆን አይችልም። ክርስቲያን የሆነ በአክራሪ ሃማኖተኛ ስም ሌሎችን መግደል ከጀመረ ያሰው ክርስቲያን ሳይሆን ሰይጣንና ዳቢሎስ የሰፈሩበት ወንጀለኛ እንጂ፤ ክርስቲያን ተብሎ ሊጠራ የማይችል ነው። ምክንያቱም መግደል በሃይማኖቱ የተከለከለ የዳቢሎስ ሥራ በመሆኑ ነው።

አክራሪነትን የምናየው ገድሎ ሃይማኖቱን በግድ ለሚያስፋፋውና ይህን በማድረጉ «በጀነት 73 ልጃገረዶች ይጠብቁሃል» እየተባለ፣ ከጠላቶቻቸው ባላይ ራሳቸውን እየጠሉ የአጥፍቶ መጥፋት ወንጀል የሚፈጽሙት ናቸው። ይህ ዛሬ በምንኖርበት የምሥራቁ ዓለም የተለመደ ክስተት ከመሆን አልፎ ፣ባህልም እየሆነ መጥቷል። ይህ ዓይነቱ ተግባር በኦርቶዶክስ ሃይማኖት ብቻ ሳይሆን፣ በሌሎችም የክርስትና ሃይማኖቶች የተወገዘና የተከለከለ ከመሆን ዘሎ፣ ወደ መንግሥተ ሰማያት በር የማያስገባ የዳቢሎስ ሥራ እንደሆነ በየጊዜው የሚሰበክ ነው።

ዛሬ በኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ ተንፈራጠው የተቀመጡ ዘመነኞች፣ ይህችን የታሪክ፣ የባህል፣የቋንቋ፣ የሥ-ነምግባር ፣ የፍትሕ፣ የአስተዳደር የሥነ-ሥዕል፣ የሥነ-ሕንፃ ጥበብ ባለቤትና አውራሽ የሆነችን ጥንታዊ ሃይማኖት ለማጥፋት የሚያደርጉት ዙሪያ ገብ አፍራሽ ጥረት ሃይማኖቱን ብቻ ሳይሆን፣ መልካም ባሕላችንም ጭምር ለማጥፋት ታጥቀው የተነሱ መሆኑን ስለሚያረጋግጥ፣ ከሁሉ በፊት የኦርቶዶክስ ሃይማኖት አማኙ ሃይማኖቴ ወይም ሞቴ ብሎ እምነቱን ለማስከበር አንድነቱን ማጠንከር ይጠበቅበታል። በሁለተኛ ደረጃ ሃይማኖቱ ከእምነት አልፎ ባህል ስለሆነ፣ የእኛነት መገለጫ ስለሆነ፣ ኢትዮጵያዊው ለማንነቱ መከበርና መጠበቅ በአንድነት እንዲሰለፍ ግድ ይለዋል። በዚህ ሂደት የቤተርስቲያኗ አባቶች የአቡነ ጴጥሮስንና የአቡነ ሚካኤልን አርኣያነት በመከተል ሕዝቡን ከነጣቂ ተኩላዎች መጠበቅ፣ ሃይማኖቷን ሊያጎድፍ የተዘጋጀውን ኃይል ሕዝቡ ተባብሮ እምነቱን እንዲጠብቅ ሳያሰልሱ ማስተማር ይጠበቅባቸዋል።

በሌላ በኩል ማተብ ይበጠስ የሚሉ ሰዎች ሐቅ ይጥፋ፣ ውሸት ይንገሥ፣ መታመን የፋራ ነው፣ አለመታመን ብልጥነት ነው(አራዳነት ነው)፣ ለዕውነት መቆም ኋላቀርነት ነው፣ ከሐሰት ጋር ማበር አዋቂነት ነው እያሉን መሆኑን ልብ ልንል ይገባል። አዎ !በሥልጣን ላይ ያሉት ሰዎች እከሌ ከእከሌ ሳይባል፣መሠረተ ባንዳ የባንዳ ልጆች ስለሆኑ ለነርሱ ሐቅ፣ዕውነት ምናቸውም አይደለም። የአገሪቱን የረጅም ጊዜ ታሪክ በመቶ ዓመት የገደቡት፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነት የካዱት፣ ባንዲራችን ጨርቅ፣ ያሉት ዕውነትን የማያምኑ፣ ሐቅን የማይቀበሉ ከሐዲዎችና ሐሰተኞች ከመሆናቸው የመነጨ ነው። ማተብ ሲበጠስ ሃይማኖት የሚበጠስ ሳይሆን፤ቀድሞ ሊበጥስ የተነሳውን ብቻ ሳይሆን፣ያሰበውን የሚበጥስ ኃይል ከሕዝቡ ጋር ያለ መሆኑን ከጌታቸው ከዳቢሎሱ መለስ ዜናዊ እና ከአባ ጳውሎስ ሕልፈተ ሞት ትምህርት ሊወስዱ በተገባቸው ነበር። ዳሩ «ያደቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይለቅም» ሆኖ ባቸው፣ የሃይማኖታችንና የእኛነታችን መገለጫ የሆነውን ማተባችን ሊቆርጡ አሰቡ። ሽፈራው በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ደም ከተጨማለቁት ሰዎች አንዱ ነው። ይህንም ማተብ የማስቆረጥ ምኞት መቃጣት እንጂ መማታት አይደለም ብለን ልንተረጉመው ፈጽሞ አይገባም። መቃጣት በራሱ ወንጀል ነው። ይህም ከወያኔ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን እስከ ወዲያኛው ለማጥፋት ለተያያዘው የጥፋት ዘመቻ አንዱ አካል መሆን አውቀን ጥፋቱ ዕውን ከመሆኑ በፊት ስለኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት የሚጮኸው ወገን ከወዲሁ መላ ማለት ይጠበቅበታል። የእጅን ለቆ መሟገት ሰማይን መቧጠጥ ነውና ማተባችን ከወዲሁ ጠበቅ ለማድረግ እንዘጋጅ!

ETHREp

 

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የ20 ሺህ ብር ዋስትና ገንዘብ ባለማስያዙ በእስር ላይ ነው

$
0
0

ኀዳር (አራት) ቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :- የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ የዕንቁ መፅሔት አዘጋጅ በነበረው ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ላይ የተሳሳተ መረጃን በመስጠት፣ ማነሳሳትና ግዙፍ በሆነ ማሰናዳት ወንጀል የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል አራዳ ምድብ ችሎት ህዳር 2 ቀን 2007 ዓ.ም ክስ

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

የመሠረተበት ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የተጠየቀውን የ20ሺህ ብር ዋስትና ማቅረብ ባለመቻሉ በቂሊንጦ በእስር ላይ መሆኑ ታውቆአል፡፡ የጋዜጠኛውን ዋስትና በመዋጮ ለመሸፈን የቅርብ ጉዋደኞቹ የባንክ አካውንት በመክፈት በዛሬው ዕለት ዕርዳታ ማሰባሰብ ጀምረዋል፡፡

የዐቃቤ ሕግ የክስ ዝርዝር እንደሚያስረዳው የቀድሞ የዕንቁ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ፤ አቶ አምሳሉ ገ/ኪዳን በተባሉ ፀሐፊ “የተገነቡትና በመገንባት ላይ ያሉት ሀውልቶች የነማን እና ለነማንስ ናቸው?”

በሚል ርዕስ ባቀረበው ፅሁፍ መነሻነት፤ ባሳለፍነው ዓመት በጅማ ዩኒቨርስቲ በሚገኙ ተማሪዎች መካከል ግጭት እንዲቀሰቀስ መንስዔ መሆኑንና በግጭቱም 30ሺህ ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን ይጠቅሳል።

ጋዜጠና ኤልያስ ማክሰኞ ዕለት ክሱን ለመስማት ፍ/ቤት በተገኘበት ወቅት የ20 ሺ ብር ዋስትና አቅርቦ እንዲለቀቅ ፍ/ቤቱ ብይን የሰጠ ቢሆንም ጋዜጠኛው ለጊዜው የሚያሲይዘው ገንዘብ በማጣቱ ቀጨኔ መድሃኒያለም አካባቢ በሚገኝ አንድ ፖሊስ ጣቢያ እንዲያድር ከተደረገ በኃላ ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት መዛወሩ ታውቆአል፡፡

የጋዜጠኛው የቅርብ ጉዋደኞችና ወዳጆች ጋዜጠኛውን ከእስር ለማስፈታት የባንክ አካውንት በመክፈት ዕርዳታ ማሰባሰብ መጀመራቸውንና የአካውንቱ ቁጥርም

የኢትዮጽያ ንግድ ባንክ የሂሳብ ቁጥር 1000097440655

Swift Code:- CBETETAA መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ፍ/ቤቱ የጋዜጠኛውን ጉዳይ ለማየት ለታህሳስ 4 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ አይዘነጋም፡፡

Source:: Ethsat

የመለስ “ትሩፋቶች” (ባለቤት አልባ ከተማ) ደራሲ፤ ኤርምያስ ለገሰ ቅኝት፤ መስፍን ማሞ ተሰማ

$
0
0

meles bookዘምረው ዝም አላሉም። ዘምረው አመፁ። አብዮት አፈነዱ፤ የእንስሳት አብዮት። በሚኖሩበት ሀገር – በእነሱ አጠራር፤ የእርሻ ጣቢያ – ለዘመናት በጭቆና ቀንበር ረግጦ ሲገዛቸውና ሲመዘብራቸው በኖረው የሰው ዘር ገዢያቸውና ግብረ አበሮቹ ላይ ሆ! ብለው ተነሱ። ቀንበር በቃን። ባርነት በቃን። ብዝበዛ በቃን። … ነፃነት እንጂ። -–[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live