Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ተስፋዬ ገ/አብ –በኤርትራዊ ጋዜጠኛ እይታ

$
0
0

ሰናይ ገ/መድህን ይባላል። በኤርትራ ቴሌቪዥን እና ሬድዮ የአማርኛ አገልግሎት ክፍል ውስጥ እ.አ.አ. ከ1998 እስከ 2011 ድረስ ሰርቷል። በዚሁ የረዥም ጊዜ የጋዜጠኝነት ሙያው ነበር ሰናይ ከተስፋዬ ገ/አብ ጋር አስመራ ውስጥ በቅርብ ለመተዋወቅ የበቃው። ዛሬ ኗሪነቱ ሜልበርን፣ አውስትራሊያ የሆነው ኤርትራዊው ጋዜጠኛ ሰናይ ገ/መድህን ለስለስ ብሎ በተጻፈ ቋንቋ አመሻሹ ላይ የሻእብያ ሰላይ መሆኑን በተረጋገጠው “የቢሾፍቱ ልጅ” እንዲህ እያለ ይተርክልናል። መልካም ንባብ።

Part 1



Author Tesfaye Gebreab

Author Tesfaye Gebreab


ተስፋዬ ከደቡብ አፍሪካ አስመራ መግባቱን አንድ ኤርትራዊ ደራሲ ወዳጄ ነገሩኝ። ያረፈዉም አስመራ ዉስጥ ከጥቂት ታላላቅ ተብለዉ ከሚታወቁትበአንዱበሆነዉሳቫናሆቴልነበር፡፡ ወዳጂከተስፋዬጋርትዉዉቃቸዉኢትዮጵያእያሉመሆኑንከገለጡልኝበሁዋላ አብረን ሄደን እንኩዋን በሰላም መጣህ እነድንለዉ ጋበዙኝ። አላቅማማሁም። በጋዜጠኝነቱና ደራሲነቱ ብቻ ብሎም ባነጋጋሪዉ የቡርቃ ዝምታ ስሙ የተነሳዉን ተስፋየን ለመተዋወቅና ለማዉጋት እንዴትስ አቅማማለሁ? በዚያ ላይ እኔም ጋዜጠኛ። ወሬ አነፍናፊ። ያልተመለሰዉ ባቡር የሚለዉን መፅሐፉን ኢትዮጵያ እያለሁ አንብቤለት ነበር፡፡ የቡርቃ ዝምታ ሲወጣ ኤርትራ ብሆንም የመፅሃፉን ይዘት በተመለከተ ጋዜጦች ላይ የተስተናገዱ የተለያዩ አስተያቶችን አንብቢያለሁ፣ ከሰዎች ጋርም ተወያይቼ ነበር። ሙሉ መፅሃፉን አላነበብኩም። ያኔ ከወዳጄ ጋር እንደወትሮዉ ሁሉ ስለ ፅሁፎቹ እየተወያየን ነበር የደረስነዉ፡፡ አልነበረም፡፡ ወዳጄ ቀጠሮ አልነበራቸዉም እዚያ ማረፉን ብቻ ከሰዉ ሰምተዉ እንግዳ ስለሆን አናጣዉም በሚል ነበር ያዘገምነዉ። ዕዉቁን ኢትዮጵያዊ የጠፈር ሳይንቲሰት ኢንጅነር ቅጣዉ እጅጉን ባልገመትኩት ሁኔታና በአድናቆት ተሞልቼ የተዋወቅኩትም ቃለመጠይቅ ያደረግኩላቸዉም እዚሁ ሆቴል ተገኝቼ ነዉ ፡፡ አስመራ በቆዩባቸዉ ጥቂት ቀናት ያረፉት እዚሁ ሳቫና ሆቴል ነበር። አብረዋቸዉ ከመጡ ሁለት ኢተትዮጵዉያን ጋር፡፡ ጊዜዉ 2004 አመጣጣቸዉና ቆይታቸዉ ሚስጥራዊ፤ የሚያዉቁትና የተገናኙትም ከፕሬዚዳንት ኢሳያስና ኮ/ል ጠዓመ (መቐለ) ከሚባለዉ ወታደራዊ ስላይ ጋር ነበር፡፡ ጌታ ነፈሳቸዉን ይማር።

እነሆ ተስፋዬ ገብረአብም እዚሁ ሆነ ያረፈዉ። አጋጣሚ ወይንስ…. ለሆቴሉ እንግዳ ተቀባይ ለተስፋየ የሚሰጥ የስልክ ቁጥር ነግረን ተመለስን። የኔንም ጭምር። በሚቀጠለዉ ቀን ተስፋየ ለኔም ለወዳጄም ደወለና ቀጠሮ ያዝን። ቀጠሮአችን እዚያዉ ያረፈበት ሳቫና ሆቴል ነበርና ከወዳጄ ጋር አብረን ሄድን። ከኔ ጋር የመጀመሪያ የትዉዉቅ ሰላምታ ከወዳጄ ጋር ደግሞ የአዲስአበባ ጥቂት የግንኙነት ጊዜያቶቻቸዉን አንስተን አወጋን። በጋለ መንፈስ የተሞላ ነበር ጨዋታችን። ተስፋየ መፅሃፍ ለማሳተም ዝግጅቱን ማጠናቀቁን / የጋዜጠኛዉ ማስታዎሻን / ስለ ስነ ፅሁፍ ሚድያ ብሎም የኢትዮጵያ ፖለቲካ ብዙ ብዙ ነገሮችን በቆይታችን አንስተናል። አስመራ ስለከተሙት የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ሃይሎች ስናወራም የዮናታን ዲቢሳ ስም ተነሳ። “ዮናታን እዚህ ነዉ ያለዉ አይደል?” ሲል ጠየቀንና መኖሩን ነገርነዉ፡፡ ሊያገኘዉ እንደሚፈልግ በጉጉት ሲያየን ወዳጅነታችንን ገለፅልነት። ችግር የለዉም ለማለት። ዮናታን በሽግግሩ ዘመን ራዲዮ ፋናን በቦርድ ሰብሳቢነት ሲመራ በነበረበት ወቅት የተስፋየ አለቃ ነበር። የቀድሞ የኢህዲን ነባር ታጋይና ከዚያም የኦህዴድ መስራችና ስራአስፈፃሚ የነበረዉ ዮናታን ኦነግን 2002 አካባቢ ተቀላቅሎ አስመራ ነዉ ያለዉ።አሁን እንኩዋን ኦነግና ፖለቲካ በቃኝ ብሎ ከኤርትራ መዉጪያ የወንድ በር እየጠበቀ መሆኑን አዉቃለሁ። በኤርትራ የ15 ዓመት ኑሮየ ካፈራሁዋቸዉ የቅርብ ወዳጆቼ አንዱ ነዉ።

በሞቀየጨዋታችንመሓልድንገትተስፋየ “በኤርትራ የጋዜጠኞችና ደራሲያን ማህበር ስለሌለ ማህበር ማቁዋቁዋም አለብን”ሲል ሃሳብ ሰነዘረ። እኔና ወዳጄ ተያየን ፡፡ “እንዲህ ዓይነት ነገር አዚህ አይወዱም አታስበዉ !” አከታትለን መለስንለት። በጥርጣሬ ዓይን መተያየታችንንም አስታዉሳለሁ፡፡

ከተስፋየ ጋር የመጀመሪያ ዕዉቂያ አድርጌ ስንመለስ ከወዳጄ ጋር ስለ ተስፋየ ጥቂት ነገሮችን አንስተናል፡፡ በተለይም ያረፈበት ሆቴል በአስመራ ዉድ ከሚባሉት አንዱ በመሆኑ “ወጭዉን እንዴት ይችለዋል ምክንያቱም ቋሚ ገቢ የለዉም፡፡ በዚያ ላይ እንደነገረን ኤርትራ ረዘም ላለ ጊዜ የመቀመጥ ሃሳብ አለዉ፤ ስለዚህ ቤት መከራየት ነዉ የሚያዋጣዉ ፡ ወይንስ ወጭዉን የሚሸፍንለት ይኖር ይሆን የሚሉ የወዳጅነት ሃሳቦችን ተለዋወጥን፡፡ “ከባለቤቱ በላይ ኣዋቂ እንትን ነዉ” ለሚለዉ ብሂል አልተጨነቅንም። የጋዜጠኛዉ ማስታወሻ የተባለዉ መፅሃፉ ኤርትራ እንደሚታተምና ገበያ ላይ እንደሚዉል የነገረንን ግን በጥርጣሬ አማነዉ፡፡ ያዉም አሳታሚዉና አከፋፋዮቹ ተቁዋማት የመንግስት (ህግደፍ) የሆኑት ሳቡር ማተሚያ ቤትና አዉገት መፃህፍት ሙዚቃና ቪዲዮ አከፋፋይ የመሆናቸዉ ነገር ተስፍሽ የህግደፍ ባለሙዋል እየሆነ ነዉ መሰል ማለታችን አልቀረም፡፡(ሁለቱም በህግደፍ ስር ያሉ የንግድ ተቁዋማት ናቸዉ)። አማርኛ መፃህፍት ሙዚቃና ቪዲዮ ኤርትራ ዉስጥ እነኩዋን ሊታተሙ እንደ ወንጀለኛ እየታደኑና እያስቀጡ ባለበት ሁኔታ ታዲያ ህግደፍ ለተስፍሽ እንዳሻህ በአማርኛዉ ገበያ ፈንጭበት ማለቱ ያለ ቃልኪዳን አልነበረም፡፡ በነገራችን ላይ ተከታዩ የደራሲዉ ማስታወሻ መፅሃፉም የታተመዉም ስርጭቱም ከዚያዉ ነዉ፡፡ የመፅሃፉ ገበያ ቅብብሎሽ የተካሄደዉም ከእዚያዉ ከአስመራ በህግደፍ ደላላነት ነዉ፡፡ ሻጭ ተስፋየ አትራፊ …፡፡ ነገርን ነገር እያነሳዉ ሄደ መሰለኝ። ተስፋየን ያረፈበት ሆቴል ሄደን ካገኘነዉ በሁዋላ ሳንገናኝ ሰነባበትን። ምነዉ ጠፋ ማለታችን ተገቢ ነበር። ምክንቱም ላገሩ እንግዳ መሆኑና በቋንቋም በተመሳሳይ የዉይይት ርዕሰ ጉዳዮችና ለሙያ ነክ ወግ እንፈላለጋለን ብለን በመጠበቃችን። ዮናታንንም አላገኘዉም። ዮናታን ግን ተስፋየን በሩቅ እንዳየዉ ነግሮኛል።
ከወር ወይም ሁለት ወር በኋላ ይመስለኛል የጋዜጠኛዉ ማስታወሻ ገበያ ላይ ዋለ። የአስመራ ዋናዉ ሃርነት ጎዳና ላይ ሳይቀር በመፅሃፍ ሻጮች ተቸበቸበ። 100 ናቅፋ። በዚያዉ ሰሞን አለቃየ ጠራኝና “የጋዜጠኛዉ ማስታወሻ መፅሃፍን በራዲዮ ትረካ ታቀርበዋለህና እንካ ቀድመህ አንብበዉ” ሲል አዘዘኝ፡፡ ሙሉ በኢንተርኔት የሚሰራጩና ረዘዣዥም ትረካ የሚያሻቸዉን ፅሁፎች ብዙ ጊዜ አንብቢያለሁ። ለምሳሌ የቀድሞ አየር ሃይል ባልደረባ የነበሩት ካፕቴን ተሾመ ተንኮሉ ያወጡትን ረዥም ግለ ታሪክ ሙሉዉን፤ የዶክተር ነገደ ጎበዜን ህገ መንግስትና ዲሞክራሲ በኢትዮጵያ በሚል ካሳተሙት መፅሃፍ አብዛኛዉን፡፡ ሙሉ መፅሃፍ በትረካ ሲስተናገድ ግን የጋዚጠኛዉ ማሰታዋሻ ለፕሮግራማችንም ለኔም የመጀመሪያ ነበር። የበላይ ትዕዛዝ ነዉ። ለነገሩ የትረካ ንባብብን በፍቅር ስለምወድ ቅር አላለኝም። በወጋየሁ ንጋቱ የፍቅር እስከ መቃብር ትረካ ፍቅር እንደተለከፍኩ አሁንም ያ የትረካ ፍቅር ዉስጤ አለና።

በአንድ ሌሊት መፅሃፉን አጋመስኩና ለቀረፃ ዝግጁ ሆንኩ።ከዚያ ስቱዲዮ ልዩ የቀረፃ ፕሮግራም ተይዞልኝ በአርቲስት ትግስት ዉብና ለስላሳ የሙዚቃ ቅንብር ሲዲ እያጀብኩ ትረካዉን ነካሁት። በተለያየ ስሜት ዉስጥእየሆንኩ፤ በሚያስቀዉ ሳቅ እየተፈታተነኝ በግነቱ እየተገረምኩ ፡፡ ከስር ከስር በቅድሚያ እየተቀረፅኩ ለአየር በቃ፤፤

ታዲያን በዚያን ሳልስት ተስፋየን ከዉጭ አገልግሎት ዳይርክተሩ አለቃችንና ከአንድ እንግዳ ሰዉ ጋር ማስታወቂያ ሚኒስቴር ካፊተርያ አየሁት። እንግዳዉን ሰዉየ አዉቀዋለሁ። ኤርትራ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ተቃዋሚዎችን በበላይነት ከሚያዙና ከሚያስተባብሩት ኤርትራዊያን ወታደራዊ የስለላ ኮሎኔሎች አንዱ ነዉ። ኮሎኔል ፍፁም ወይንም በቅፅል ስሙ ( ሌኒን )። ኮሎኔል ፍፁም ከእኛ ክፍል ጋር በቅርብ ስለሚሰራ በሚገባ እንተዋወቃለን። ሶስቱን አንድ ላይ እንዳየሁዋቸዉ የእለቱ ጉዳይ ወዲያዉ ገባኝ። ከጥርጣሬ በላይ። ይሄዉም አለቃችን ኮሎኔሉንና ተስፋየን ለተልዕኮ እያስተዋወቀ ነዉ። ምክንያቱ ደግሞ የተስፋየን መፅሃፎች ወደ ኢትዮጵያ በድንበር በድብቅ ማሻገርና ማሰራጨት ። ኮሎኔሉ በእኛ ፕሮግራም የተላለፉ የተለያዩ የፕሮፓጋንዳ ህትመቶችና ዲቪዲዎችን በታማኝ ኢትዮጵያዊያን ተቃዋሚዎች አማካኝነት በድንበር ማሸጋገሩን አዉቃለሁ። ይሄዉ ተስፍሽም ከኤርትራዊያን የስለላ ኮሎኔሎች ጋር የሚስጥር ግንኙነቱን ሲያደርግ አየሁ። ከግንኙነቱ በሁዋላ ቢያንስ የአማርኛዉ ክፍል ጋዜጠኞችን ሰላም ይለናል ብለን ጠብቀን ነበር አላደረገዉም። ከኮሎኔል ፍፁም ጋር መገናኘቱ እንዲታወቅበት አልፈለገም ይሆናል። ማንም ልብ እንዳላለዉ አይነት ሹልክ ብሎ ወጣ። እርግጠኛ ነኝ ካፌቴርያ ከነበርነዉ ዉስጥ ከእኔ በቀር ተስፋየ ገብረአብ መሆኑን ያዋቀ አልነበረም። በግርምት ኣሻግሬ እያየሁ ነበረና ከሄዱ በሁዋላ አብረዉኝ ለነበሩት “ከአለቃችንና ኮሎኔል ጋር የነበረዉ ተስፋየ ገ/አብ ነዉ ስላቸዉ” የቱ የቱ ብለዉ ተከታልለዉ ወጡ።ተስፋየ ፈጥኖ የኮሎኔል ላንድክሩዘር ላይ ተሳፍሮ ሄዱዋል። ከዚህ በሁዋላ ተስፋዬ ለገዥዉ ፓርቲ ቅርበት ያለዉ መሆኑን ለመገመት አዋቂ ቤት መሄድ አላሻኝም፣ ገና ከጅምሩ ማለት ነዉ፡፡

የጋዜጠኛዉ ማስታወሻ ትረካ በተከታታይ ሁለት ሶሰት ዕሁድ ዓየር ላይ በዋለ ሰሞን ተስፋይ ቢሮ ስልክ ደወለልኝና ቀጠሮ ያዝን፡፡ ኒያላ ሆቴል አመሻሽ ላይ ተገናኝተን ገና ሰላምታ ሳንጣገብ ስለመጽሃፉ ትረካ አድናቆቱን አዥጎደጎደዉ። በነገራችን ላይ አንተ ነህ አይደል የምትተርከዉ? እስከተወሰነ ጊዜ ድረስ በፐሮግራሞቻችን የአቅራቢ ስም አይገለጥም ነበርና ሰዎች ቢደነጋገሩ አይገርመንም ነበር፡፡ ተስፍሽን ግን እንዴት አወቅ አላልኩትም፡፡ “እኔ ከጻፍኩት በላይ እያጣፈጥክ ያንተ ወግ እሰኪመስል ድረስ ነዉ እየተረከዉ ያለኸዉ”፡፡ ከትረካዉ እየጠቃቀሰ ወጉን በጂን ያወራርድዉ ያዘ፡፡ እኔም ከታሪኮቹ እያነሳሁ እየጣልኩ የምሽቱን ጨዋታ አጀብኩት፡፡ በይዘቱ ላይ መነጋገሩን አልፈለግኩም፡፡ የማልስማማባቸዉ ቢኖሩም፡፡ ትረካዉን በተመለከተ ግን ባድናቆቱ ዉነት ዉነት ሙቀት በሙቀት ሆንኩላችሁ። የአማርኛ ስነ ጥበብ የጠማዉ ኤርትራዊም በትረካዉ እየረካ መሆኑን ከግራም ከቀኝም በቀጥታም በተዘዋዋሪም ከምናገኘዉ ወሬ ላይ የባለቤቱ በላዩ ለይ ሲታከልበት …፡፡ ለነገሩ ሳካብድ ነዉንጂ የህዝባዊ ግንባር ፖለቲካ እጅ እጅ ላለዉና የአማርኛ ሙዚቃ እንዳይሰማ እግድ ለተጣለበት ኤርትራዊ ትረካዉ ፍቱን መዝናኛዉ ቢሆን ምን ይገርማል አትሉም።

ከዚያ በሁዋላ ከተስፍሽ ጋር ያለቀጠሮ ቁዋሚ ተሰላፊ ከሆነበት ኒያላ ሆቴል መገናኘታችን ልሙድ ሆነ፡፡ ዋል አደር ሲል በተደጋጋሚ ከዉስን ኤርትራዉያን ወጣቶች ፀሃፍት ጋር አገኘዉ ጀመር። በህግደፍ ስር የሚሰሩና የዘመኑ ተጠቃሚ የሚባሉ ናቸዉ። በጭፍን የህግደፍ ደጋፊነታቸዉ ይታወቃሉ። ህግደፍ ጠቀም ያለ አበል የሚቆርጥላቸዉ ወጣት ምሁራን በብዛት አሉ። አብዛኛዎቹ (ሁሉም እንበል) ደርግ ከኤርትራ ሲባረርና ህግደፍ ሲገባ የአስመራ ዩኒቨርስቲ የነበረበትን የተማሪ ርሃብ ያስታገሱ ናቸው። ከ1.00 -2.00 ነጥብ ለዲግሪ ገብተዉ ገዋን ለብሰዉ የወጡ። ኢነጅነር ዳኛ…ሆነዋል። አንዱ በህግደፍ የበላይነት የሚታተመዉ ሀዳስ ኤርትራ ጋዜጣ አከፋፋይ ነዉ። ሌላኛዉ የህግደፍ ወጣቶች ማህብር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ነዉ። ሌላኛዉም… ተስፋየም ወደ ቢጤዎቹ ተጠጋ ማለት ነዉ፡፡ ተስፋዬ ያለከለላና መከታ መኖር አይችልምን የምትል ነገር ወጋ አደረገችኝ። በአማርኛ ካለዉ ተወለድ ወይ ካለዉ ተጠጋ የሚለዉን ብሂል ልብ ይሉዋል፡፡ በትግርኛ ደግሞ ተመሳሳዩ ሲኖር ካለዉ ተጠጋ የሚለዉን ወደ ጋራ ተጠጋ ይሉታለል ( ….ናብ ጎቦ ተፀጋእ )። በወታደራዊ አባባል ገዥ መሬት ያዝ እንደማለት ነዉ።፡ስለዚህ ተስፍሽ ገዥ መደቡንም ካዝናዉንም እንዴት መጠጋት እንደሚችል ጥሩ አድርጎ ለምዶታል ማለት ነዉ። ግን ከረፈደ ነዉ ህግደፍን የሙጥኝ ያለዉ። ምክንያቱም ህግደፍ ራሱ ከለላ ፍለጋ ኩዋታርን ኢራን እጅ በሚያይበት አይዞህ ባዩን ጋዳፊን በዉርደት ባጣበት ብሎም ያየነፃነት ፋኖነቱ እንደጉም በበነነበትና በወገኖቹ ኤርትራዊያን ሳይቀር አይንህን ላፈር በተባለበት ጊዜ ነዉና የተጎዳኘዉ። ነገርን ነገር ካነሳዉ ዘንዳ ተስፋዬ እርም ኤርትራዊ ብሎ ኦሮሞነትን የሙጥኝ ያለዉ ለዚህ ይሆን? ምክንያቱም በክፉ ጊዜ ህግደፍን መወዳጀቱ በብዙ ኤርትራዊያን ሙሽሙሽ (የማይረባ ) መባሉን መቼም ሳይሰማ አይቀርም። እዚች ላይ እንዲያዉም ለኢሳያስ

(ተስፋዬ ገብረአብ)

(ተስፋዬ ገብረአብ)

አፈወርቂ የቀኝ እጅ ከሆኑትና ለብዙ በኤርትራ ለሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ተቃዋሚዎች ደብዛ መጥፋት (ኮ/ል ታደሰ ሙሉነህን) ጨምሮ ተጠያቂ ከሆኑት ቁልፍ ወታደራዊ ስለላ ኮሎኔሎች ከአንዱ ከ ኮ/ል ዮናስ ሴት ልጅ ጋር ጋብቻ ቢጤ መስርቶ ልጅ መዉለዱን ጠቆም ብናደርግስ? ጋብቻዉ በኣጋጣሚ ከልብ ለልብ ፍቅር ነዉ ወይንስ ፖለቲካዊ ጋብቻ? በየዋህነት እንለፈዉ ይሆን ከሆነ የግጥምጥሞሽ ነገር እንላለን ግና የህዝባዊ ግንባርን አያሌ ፖለቲካዊ ጋብቻዎች ስንመነዝር ( ኢሳያሰ ራሳቸዉ በትግሉ ዘመን ሆነ ብለዉ ገደሉት የሚባለዉን የአካለጉዛይ ተወላጁን ታዋቂ አመራር አብረሃምን አካባቢ ሰዎች ለማስደሰትና ለመያዝ የአካለጉዛይ ተወላጅ የሆነችዉን ታጋይ ሳባ ሀይሉን አግብተዉ መዉለዳቸዉን ማጣቀሻ ስንመዝዝ ፡፡ከሳባ በፊት የሃማሴን ልጅ የነበረችዉ ሚስታቸዉ አሁንም አስመራ እንደምትገኝ በመዘከር ነዉ) ኢሳያስ ፖለቲካዊ ጋብቻቸዉ እየኮሰኮሳቸዉ ሳይሆን ይቀራል በአደባባይ የሚማግጡት፡፡በፍቅር ላይ ያልተመሰረተ ጋብቻ እንዴት አይኮሰኩስ። ነገርን ነገር እየመዘዘዉ የጎንዮሽ እየነጎደ ተቸገርኩ እኮ ጃል! ስለዚህ ተስፍሽም ጋብቻዉ ፖለቲካዊ ሆኖ የወደፊቱ የኤርትራ ኑሮ ከኮሰኮሰዉና እነ ወዳጁ ዳዉድ ኢበሳ በለስ ከቀናቸዉ ኦቦ ተብሎ ደብረዘይት ለመመሸግ ቀብድ መክፈሉ ይሆን! ሰዉየዉ እኮ ተስፍሽ ነዉ ፡፡
በነገራችን ላይ ተስፋየን ምነዉ የነዳዉድ ኢብሳ ብቻ ወዳጅ አደረከዉ የሁሉም ኦሮሞ ወዳጅ አይደለምን የሚል ጠያቂ እንደሚኖር አስባለሁ፡፡ ለዚህ ትዝብት ቢኖረኝ ነዉ፡፡ በቀጣይ እማቀርበዉ፡፡
*ተስፋየ ብ/ጄኔራል ከማል ገልቹ ሌላ አሁን ስሙን የማልገልጠዉ ሰዉ እና እኔ ሆነን ያደረግነዉ ጭዉዉት። *የተስፋየ የአስመራ ኒያላ ሆቴል (የመንግስት ሆቴል ነዉ ) ሃድራዉና የጂን ላይ ወጎች
*ተስፋየ የኢትዮጵያን ሪቪዉ ኤልያስ ክፍሌና የእኔ የአንድ ሰሞን ድርድሮች
*የወግ ገጠመኞች ነገር ከተነሳ ተስፋየና እኔ ካነሳናቸዉ ከጣልናቸዉ የታዘብኩትን (እሱም ታዝቦኝ ይሆናል ) *የደራሲዉ ማስታወሻ ላይ ካሉት ባለታሪኮች ፡ ኮ/ል አለበል አማረ ሌ/ኮ/ል አበበ ገረሱ እና የወሎዉን ባለታሪክ የመሳሰሉትን የዘከርኩትን እያስታወሰኩ በቀጣይ ላወጋችሁ አስባለሁ ፡፡

የዚያ ሰዉ ይበለን
ሠናይ ገብረመድህን (ጋዜጠኛ) አዉስትራሊያ ፣ሜልበርን ጥቅምት 2007


ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ

$
0
0

ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ

አንተነህ መርዕድ

ህዳር 2014

በዙህ ጉዳይ ላይ ለመጻፍ በሁለት ምክንያቶች ከራሴ ጋር ብዙ ታግያለሁ። መጀመርያ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም አይደለም ለራሳቸው፤ ለሌላም የሚተርፍ አንደበት አላቸውና ራሳቸው መልስ  ይስጡ በማለት ሲሆን ሁለተኛው ምክንያቴ ደግሞ ትልልቅ አገራዊ ጉዳይ እያለ በዚህ ጠባብ ነገር መጠመድ ለማን ይበጃል በሚል ነበር።በሁለቱም ትክክል አልነበርሁም። ፕሮፌሰር መስፍን በግል ደረጃ የወረደ እንቶ ፈንቶ መግባት ስብዕናቸው ስላልፈቀደ ንቀው መተዋቸው ትክክል ነበር። በሌላ በኩል ደግሞ አንዳንድ ግለሰቦች ሆነ ቡድኖች ትልልቅ የአገር አድባሮችን ሲያዋርዱ በዝምታ መመልከቱም ተገቢ አለመሆኑን ተገንዝቤአለሁ።

Prof. Mesfin

አንድ ህብረተሰብ ከመካከሉ የሚወጡ ፋና ወጊ መሪዎችን በመንከባከብ፤ ሲሳሳቱ በማረም  ቢያሳደግ ለበለጠ ሰላምና ብልጽግና ያበቃዋል። ይህንን እውነት በበርካታ አገሮች አይተናል።በህይወት ሳሉ ተሞግሰውና ተከብረው፤ እውቀታቸውንና ጉልበታቸውን የበለጠ ለአገራቸው ጥቅም ላይ እንዲያውሉ ሲበረታቱ፣ ከሞቱም በኋላ ሃውልትና መታሰብያ ተሰርቶላቸው ትውልዱ አርዐያቸውን እንዲከተል ይደረጋል። እንዳለመታደል ባለፉት አርባ አመታት በአገራችን በአምባገነን መሪዎችና አንዳንድ ወገኖች የተያዘው አደገኛ መንገድ የአገሪቱን ትልልቅ ሰዎች ማዋረድ፣ መሪና ምሳሌ የሚሆነን ማሳጣት ነው። በተለይም በአብዮቱ ዘመን የምስራቁን ርዕዮት በአገራችን ለመትከል ታጥቀው የተነሱ ወገኖች ትልልቅ ኢትዮጵያውያንን ኢላማ አድርገው እንደነበር የምንዘነጋው አይደለም። ብዙ ለአገራቸው አስተዋፅዖ ያደረጉ አዛውንትና ትልልቅ ዜጎች ራሳቸውን ትልቅ አድርገው በሚመለከቱና ትንንሽ ጭንቅላት ባላቸው ከንቱዎች ተሰድበዋል፣ ተዋርደዋልም። እነዚህ ብርቅ ኢትዮጵያውያን  ከትውልድ ትውልድ ሊተላለፍ የሚችል ስራቸው በሁሉም ልቦና ያለ ሲሆን ሰዳቢዎቻቸውና አዋራጆቻቸው ግን ያሰቡት ሳይሳካ መክነው ቀርተዋል።

ዛሬ በህይወት የሚገኙትና በአዛውንት እድሜአቸው ደከመኝ ሳይሉ በተባ አንደበታቸው ጥልቅ የሆነ እውቀታቸውንና ተመክሮአቸውን ለወገን እያበረከቱ ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም  ብዙዎች የምንሳሳላቸውና የምናከብራቸው ቢሆንም ሁሉም ይወዳቸዋል ብለን አንጠብቅም። ሶስቱንም የአገራችንን   የአምባገነን ስርዓቶች አጥብቀው የታገሉ፣ ድፍረትና እውቀታቸው የመጠቀ፣ ለሃብት፣ ለስልጣን ሆነ ለግል ድሎት ቦታ የማይሰጡ፣ ትክክል ነው ብለው ያመኑትን ከመናገርና ከማስተማር ግንባራቸውን የማያጥፉ መሆናቸው ለብዙው ኢትዮጵያዊ እንደ አርአያ (ሮል ሞዴል) ሆነው እንዲታዩ ያደረጋቸውን ያህል በአንዳንዶች የአገርና የህዝብ ጠላት ሆነው እንዲታዩ ጥረት ይደረጋል። ይህ ትችቴ የፕሮፌሰር መስፍንን አንዳንድ ሃሳቦች በሃሳብነት የሚሞግቱትን ጨዋ ሰዎች አይመለከታቸውም። መስፍን ወልደማርያምን ፍጹም ናቸው የሚል ሃሳብ አይወጣኝም፣ እሳቸውም ይህንን እንደማይቀበሉ አምናለሁ። ትችቴ ፈረንጆች “ህፃኑን ከእጣቢው ጋር መወርወር” እንደሚሉት ሁሉ የፕሮፌሰሩን የተወሰነ ሃሳብ በስህተትነት ይዘው ጨዋነት በጎደለው ሰብዕናቸውን ለማጥፋት የዘመቱ ወገኖች ዓላማቸው አደገኛና አጥፊ መሆኑን ለማስገንዘብ ነው።

የፕሮፌሰሩን አንዳንድ ሃሳብ የማይቀበሉ የተወሰኑ ግለሰቦች ጽሁፎቻቸውንና ንግግሮቻቸውን እየነቀሱ ጨዋነትና እውቀት ላይ የተመሰረተ ትችቶችን ማድረጋቸው ለብዙዎቻችን እውቀት መዳበርና የሃሳብ ጥራት ገንቢ ሚና ተጫውተዋል። ፕሮፌሰር  መስፍን ወልደማርያምም የምርምርና የእውቀት  ሰው በመሆናቸው ይህንን ዓይነት ትችት እንዲዳብር የሚስማሙበት ይመስለኛል። የብዙዎችን ላቆየውና በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ካንድ ወገን የሚሰነዘረው ከባህላችን ውጭ የሆነ ዓላማው ግልጽ ያልሆነ ስድ በሚያሰኝ የመንገድ አዳሪ ቋንቋ የስድብ ውርጅብኝ  በኒህ አዛውንት አባት ላይ ሲወርድባቸው ዝም ብሎ መመልከቱ ለህሊና ይከብዳል።

ነሃሴ 25 ቀን 2006 ዓ ም  “ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት”  በራሱና በሌሎችም ማህበራዊ ድረገፆች “ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በዐማራው ቁስል ላይ ጨው ነሰነሱ! የ<<ዐማራ የለም>> አቋም የክህደት ወይስ የመሳት?” በሚል ርዕስ የበተነው መግለጫ ተልዕኮው ምን እንደሆነ ያልለየና አሳዛኝ ነበር። በዚህ አምስት ገጽ በሞላ አማራው ላይ ስለደረሰ ግፍ በሚዘረዝር እውነትን ባዘለ ይዘቱ ላይ ተቃውሞ የለኝም። በመሬት ላይ ያለው ተጨባጭ እውነት ከዚያም የከፋ በመሆኑ ማንም ሊያደበዝዘው አይቻለውም። ነገር ግን በፕሮፌሰሩ ላይ የተሰነዘረው ቃል ተገቢ አልነበረም።

መለስ ዜናዊ ኢትዮጵያዊ የሆኑ ትልልቅ ሃሳቦችንና ሰዎችን አኮስምኖና ገድሎ የራሱን ትልቅነት ለመገንባት ሲጥር ለመጀመርያ ጊዜ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያምን ነው በቴሌቪዥን ሊሞግት የሞከረው። ሁሉም እንደተከታተለው በክርክሩ ወቅት የመለስ ትንሽነት ነበር ጎልቶ የወጣው። በዚያ ውይይት ኢትዮጵያውያንን በጎሳ ከፋፍሎ ሊበትን ያሰበውን ዓላማ በመስፍን ወልደማርያም አፍ ላይ ሊያስቀምጥ ሲል “አማራ የሚባል ጎሳ የለም” ብለው በስሙ እንዳይነገድበት ያቀረቡት መከራከርያ እስከዛሬ ድረስ ወያኔ በሰፋላቸው የጎሳ እጀጠባብ ማጌጥ የሚፈልጉ ሁሉ የሚያመነዥኩት ሃሳብ ሆኗል። በቅርቡ ፕሮፌሰሩ በሸገር ሬድዮ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ይሄው ሃሳብ መደገሙ ካስቆጣቸው ወገኖች ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት አንዱ በመሆኑ ይመስላል ይህንን መግለጫ አይሉት ስድብ አሰራጭቷል። ባከታታይም የሞረሽ ደጋፊዎች ነን የሚሉትም ትኩረታቸው ቆምንለት የሚሉት አማራ ነፃ የሚወጣበትን መንገድ ከመሻት ፕሮፌሰሩን በመተቸት ተጠምደዋል።

ተደጋጋሚ የሆነ ከሃሳብ ይልቅ በግል ሰብዕና ላይ ያተኮረ ትችት አስነዋሪ ከመሆኑም በላይ ፕሮፌሰሩን በመሳሰሉ ታላላቅ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚሰነዘረው ስድብ በአገር ላይ እንደሚሰነዘር ይቆጠራልና በዚህ መግለጫ ያነበብሁት ስድብ አሳዝኖኝ ከበርካታ ጓደኞቼም ጋር ተነጋግረንበት አልፈነው ነበር። እንዳጋጣሚ በፈረንጆች አቆጣጠር መስከረም 7 ቀን 2014 በቶሮንቶ ካናዳ የኢትዮጵያውያንን አዲስ ዓመት በክሪስቲ አደባባይ እናከብር ነበርና ብዙ ህዝብ በሚርመሰመስበት የደመቀ በአል መሃል የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት መሪ የሆኑትን አቶ ተክሌ የሻውን አገኘኋቸው። ደስ ብሎኝ ራሴን ካስተዋወቅሁ በኋላ በወጋችን መሃል በቅርቡ ከወጣው መግለጫቸው አምስት ገጽ እውነት ውስጥ ጨዋነት የጎደለው ስድብ ተገቢ እንዳልነበር ነገርኳቸው። የሰማሁት መልስና ለፕሮፌሰሩ ያላቸው ጥላቻ አስደነገጠኝ። ለአማራው ህዝብ መብት ቆሜያለሁ ብለው አደባባይ የወጡ  እኒህ ሰው አንዱን ታላቅ ወገናቸውን በሰብዕናቸው ገብተው ሲዘልፉ መመልከት ዓላማቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ሆኖ አገኘሁት። ስልሳዎቹ ውስጥ የሚሆኑ እኒህ አዛውንት ሌላው በእድሜ፣ በእውቀትና በተመክሮ ለሚበልጧቸው ክቡር ሰው የሚሰጠውን የጨዋ አማራ ባህል ከውስጣቸው አላየሁም። ስለሆነም ውይይቴን ብቀጥል የበለጠ ህሊና የሚያቆስል ነገር እንደምሰማ በመገመት ተሰናበትኋቸው። የመግለጫውን ስድቦች ነቅሼ ላቅርብላችሁ። (ሙሉውን ጽሁፍ ከሞረሽ ወይንም ከሌሎች ድረገጾች ፈልጋችሁ አንብቡ)

“…የፕሮፌሰር መስፍንም ክርክር ጭፍን ክህደት ወይም መሳት (መጃጀት) አልያም ቀቢፀ-ተስፋ የተሞላው ቁጭት ከመሆን አያልፍም።……ከመሳት (መጃጀት) የመነጨ ከሆነ ግን አያድርስ! እንዲህ እስኪሆንስ ፈጣሪን “አታቆዬን” ከማለት ሌላ ምን ይባላል።

“…ፕሮፌሰር መስፍን ክህደት የመታወቂያ ባህሪያቸው ስለሆነ…..”

“….ከክህደት ባህሪ በተጨማሪ በዕድሜ መግፋት ምክንያት የመጣ፣ የኋላን ያለማየት እና የመሳት አባዜ የገጠባቸው መሆኑን የሚያመለክት ነው።….”

(ስርዞቹ ለአፅንዖት የተጠቀምሁባቸው የእኔ ናቸው)

ስድቦቹ ሲጠቃለሉ ሁለት ፀያፍ ጽንሰ ሃሳብ ይዘዋል፤ ክህደትና መሳት(መጃጀት)

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያምን በክህደት መክሰስ በጣም የሚያሳዝን ነው። መስፍን ወልደማርያም ሁሉንም ኢትዮጵያዊ አማራ፣ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ ወላይታ፣ አገው፣ ጃንጂሮ፣ ጉሙዝ ሳይሉ ርሃቡን፣ ጥማትቱን፣ ስቃዩን፣ እስሩን፣ ግድያውን፣ ግርፋቱን፣ እንግልቱን በጠረጴዛ ዙርያ ውይይትና መግለጫ በማውጣት ሳይሆን ውስጡ ሆነው የታገሉትና የሚታገሉትም። ስቃዩን በአካልም በመንፈስም የሚጋሩት ጀግና ናቸው። ያውም እንደ እኔ የወያኔ ጫና ወላፈኑ ሲዋጀው ነፍሱን በጨርቁ ቋጥሮ፣ ጅራቱን ቆልፎ ከአገሩ የሸሸ ይቅርና፤ አገር ውስጥ ዳፋውን እየተጋቱ ያሉትም መስፍን ወልደማርያምን በክህደት አይወነጅሉም። እዚህ ሆኖ ማቅራራትና እዚያ ሆኖ ህዝብ መሃል እየኖሩ፣ እየተለበለቡ፣ እየታሰሩ  መታገል የብርሃን ዓመት ያህል ይራራቃልና። ርቆም ቢሆን ትግልያስፈልጋል ብሎ ላመነ ትግሉን በእውነትና በጨዋነትየተመራ ቢያደርገው የተመረተ ያደርገዋል።

የትግራይና የወሎ ህዝብ በርሃብ ሲረግፍ ሁሉም ጭንቅላቱን አሸዋ ውስጥ እንደከተተ ሰጎን አንገቱን በደፋበት በዚያ ፈታኝ ወቅት ህይወታቸውን አዳጋ ላይ ጥለው የደረሱላቸውና ዓለም እንዲያውቀው ያቀናበሩት ፕሮፌሰር መስፍን መሆናቸውን መካድ ነው ከሃዲነትሊሆን የሚችለው። የዐማራ ነገድ አለ የለም የሚል እንቶ ፈንቶ ለፖለቲካ ነጋዴዎች እንጂ ለመስፍን ወልደማርያም ሆነ ለዐማራው አንዲት ነገር አይፈይድም።

ለነገሩማ ታምራት ላይኔ፣ ተፈራ ዋልዋ፣ አዲሱ ለገሰ፣ በረከት ሲሞን፣ ደመቀ መኮንን፣ አለምነው መኮንን….አማራው አለ ይላሉ እኮ! የሚያዋርዱት፣የሚገድሉትና የሚያስገድሉት ደግሞ እነሱ ናቸው። ተግባር እንጂ መናገር ማንነትን የማያሳይ ለመሆኑ እነዚህ ሰዎች ጥሩ ምሳሌዎች በመሆናቸው፤ የሚለፈልፉትን ሁሉ ማመን ከባድ የሚሆነው ለዚህ ነው። ዲያቪሎስም ከወንጌል ይተቅሳል ይላሉ በመኖር ተመክሮ የበሰሉ ዘመዶቻችን።

በደኖ፣ አርባ ጉጉ፣ ጋምቤላ፣ አሶሳ፣ ጎንደር አደባባይ ኢየሱስ ወዘተ…አማራው ሲጨፈጨፍ በእውቀታቸው፣ በገንዘባቸው፣ በጉልበታቸው የደረሱለት፤ በአገርም በዓለምም የሞገቱት፣ ባቋቋሙት የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብት ጉባኤ (ኢሰመጉ)ና በግላቸው የደከሙትን ብርቅዬ ታጋይ ሲደክሙ ከጎናቸው ያልነበሩ በከሃዲነት ሊወነጅሏቸው የሚያስችል የሞራል ብቃት ያለ አይመስለኝም። ሙሾ ማውረድ ለእንደኔ አይነት ደካሞች ቀላል ነው። በተለያየ መንገድ ደም መላሽ የሆኑትን ጀግኖችና ትልልቆችን በመጥለፍ ጀግናና ትልቅ መሆን የሚገኝ የሚመስላቸው አይጠፉም። ከዚህ በፊትም ነበሩ። የኋላ ኋላ መጋለጡ ግን የማይቀር እውነት ነው።

ወያኔ ኢትዮጵያን ለመበተን በመድረክ ሲያውጅ፤ ይህንን ዘረኛና ከፋፋይ ዓላማ በብቸኝነት የተቃወሙት ታላቁ ኢትዮጵያዊ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ነበሩ። በዚያም አልቆም ብሎ በአማራው ላይ እልቂት ሲታወጅና ሲታረድ ያ ትልቅና ኩሩ ህዝብ መገደል የለበትም ብለው ከፊት የቆሙትና ለመስዋዕት የቀረቡት የቁርጥ ቀን ልጅ አስራት ወልደየስ ናቸው። ወያኔ ደመኛ ጠላት አድርጎ ሊያጠፋቸው ሲነሳ እንዲወግራቸው ደንጋይ ሲያቀብሉ የነበሩት “ለአማራ ቆሜአለሁ” ብለው ብቅ ሲሉ ደግሞ ታሪክና ህዝብ በትዝብት እየመዘገበ መሆኑን ሊዘነጉት አይገባም። ፕሮፌሰር አስራትን ወያኔና ደጋፊዎቻቸው በአካል እንዲጠፉ አድርገው ይሆናል፤ በስራቸው በህዝብ ልብ ላይ መሆናቸውንና ባለታሪክነታቸውን የሚያጠፋ የምድር ሃይል አይኖርም። በተመሳሳይ ሁኔታ የመስፍን ወልደማርያምን ስራና ትልቅነት ደካሞች የሚያጠፉ መስሏቸው ከሆነ ከታሪክ ሊማሩ ይገባል።

 2

( ሰዳቢዎቻቸው ይህን እስኪመስሉ በእስር ካንገላታቸው ወያኔ የሚለዩት በምን ይሆን?አክባሪዎቻቸውም ይሸልሟቸዋል)

መስፍን ወልደማርያም ትናንት ለነበረው አምባገነን መንግስት ካድሬ ሆነው አገልግለው ዛሬ ታጋይ ሆነው ብቅ ያሉ ሳይሆን አሁን ከእንቅልፋቸው ባንነው “አማራ ተበደለ” ብለው ከሚጮሁ ወገኖች በፊት በተደጋጋሚ አምባገነን ስርዓቶችን ተጋፍጠው ህዝቡ መራቡን ያጋለጡ፣ ለእርዳታ ማንም ሳይደርስ የደረሱ፤ ታሰረ፣ ተገረፈ፣ ተገደለ የተባለውን ቀድመው በመገኘት የታደጉ የተግባር ሰው ስለሆኑ በጠረጴዛ ዙርያ ለሚታኘክ የብሄር ብሄረሰብ ቲዎሪ ጊዜ የላቸውም። ስብዕናቸውና ትልቅነታቸው ወደዚህ ትንንሽ ነገር አይመራቸውም። አማራው ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ ራሱን በመስዋዕትነት ካስቀመጠበት ልዕልና አውርዶ በጠባቡ የብሄር ስልቻ ውስጥ ለመክተት የሚታገሉ ወገኖች አላማቸውን በጨዋነት ማስረዳት እንጂ በተራ ብልግና ትልልቆችን ማዋረድ “የቆሙለት” የአማራው ባህልም አይደለም።

ሌላው ፀያፍ የሆነው ሁለትኛው ስድባቸው መስፍን ወልደማሪያምን የሳተ (የጃጀ) በሚል ለማዋረድ የሰነዘሩት ስድባቸው ነው። ምን ዐይነት ጤነኛ አዕምሮ ያለው ነው በጎንደር፣ በጎጃም፣ በወሎ፣ በሸዋ የሚገኝ አማራ ብቻ ሳይሆን ሌላውም ኢትዮጵያዊ ፊት እድሜ የጠገበን የአገር አዛውንት የጃጀ ብሎ ደፍሮ የሚሳደብ? ጃጅተውስ ቢገኙ ምን ነውር አለው? በአባቱ ገበና የሚስቅ ምን ዓይነት እርጉም ነው? እንደ አገሬ ደንጋይ ምንም ሳይሰሩ ተጎልተው የሸበቱ ሠርቶና ደክሞ ያረጀን፣ የጃጀን ይንከባከቧል እንጂ አደባባይ ለስድብ ያቀርቧል?

የሚገርመው መስፍን ወልደማርያም ለመጀመርያ ጊዜ መለስ ዜናዊን ስለ አማራው የተከራከሩት የዛሬ ሃያ ሶስት ዓመት በግምት በአሁኑ ሰዓት አቶ ተክሌ የሻው ባሉበት እድሜ ላይ ሆነው ነው። የዛን ጊዜ መስፍን ወልደማርያም ይህንን ሃሳብ የተናገሩት አርጅተውና ጃጅተው ነው ከተባለ አቶ ተክሌ የሻው ሆኑ ጓደኞቻቸው ተስፋ የላቸውም ማለት ነው። ይህንን ስድብ የጻፉት ሆነ መግላጫ ሆኖ እንዲወጣ ያደረጉት ጃጅተዋል ማለት ነው። በእነሱ አባባል ከሆነ ማለቴ እንጂ እኔ ማንንም በእግዚአብሄር አምሳል የተፈጠረ ሰው በእድሜውና በጤናው የመሳለቅ ብልግና ነውርነቱን እየሰማሁ ነው ያደግሁት። ነገር ግን መስፍን ወልደማርያም  በአሁኑ እድሜአቸው እንኳ ከነአቶ ተክሌ ሺህ ጊዜ የሰላ አዕምሮ እንዳላቸው አውስትራልያ ሰሞኑን ያወያዩአቸውን ኢትዮጵያውያንን በመጠየቅ መረዳት ይችላሉ። ወይንም ፕሮፌሰሩ በየቀኑ በብሎጋቸው የሚያሰፍሩትን ማንበብ አለባቸው። አንድ ኢሜል መመለስ ባህል ማድረግ አቅቶን በምንደፋደፈው ደካሞች መካከል ቀን በቀን የዓለምን ሁኔታ እየተከታተሉ ብዙዎቻችንን እያስተማሩ ያሉ አዛውንት ጃጅተዋል ማለት ምን ተፈልጎ ነው? በነፃው ዓለም ትልልቅ ከተሞች ሃያ ሰው አሳምኖ መሰብሰብ የማይችሉ ሰዎች የመስፍን ወልደማርያምን አዕምሮ ለመመዘን ሲሞክሩ ያሳዝናል። ባዶ በርሜል ብዙ ይጮሃል ብለው ይሆናል መስፍን ወልደማርያም መልስ ያልሰጧቸው። እውቀት በተግባር ይፈተኗል። ለአማራው አለህ የለህም የሚለው ቀረርቶ ጀሮው ጫፍ አይደርስም። የመንዝ አማራ ከቀዳማዊ ኃይለስላሴ ሃረጉን ቢስብ እንደማይጠቅመው አሳምሮ ያውቃል። እንዳይገደል፣ እንዳይታሰር፣ እንዳይዘረፍ በተጨባጭ የሚከላከልለት እንጂ በስሙ የንግድ ፈቃድ አውጥቶ የሚነግድበት አይደለም የሚፈልገው። ስለፕሮፌሰር መስፍን ገድል ብዙ የሚያውቁ፣ አብረው የሰሩ፣ ሃዘናቸውንና ድካማቸውን የተካፈሉ ዝም ብለው በተቀመጡበት ሰዓት አላስችለኝ ብሎ ለፈለፍሁ እንጂ ታሪክና በርካታ አዋቂዎች እየታዘቡ እንደሆነ አውቃለሁ።

ለፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በእግዜብሄር አምሳል የተፈጠረ ሰው ክቡርነቱ እንጂ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ፣ ወላይታ… የሚለው የታፔላ ስም መቀነስ መጨመሩ ፋይዳ አይሰጣቸውም። ለከፋፋዮች፣ ለፖለቲካ ነጋዴዎች፣ የማንነት ቀውስ ውስጥ ለተዘፈቁ ከንቱዎች ይጠቅም ይሆናል። እየጠቀመም ነው።

አፄ ቴዎድሮስን፣ አፄ ዮሃንስን፣ አፄ ምንይልክን፣ ንጉሥ ተክለሃይማኖትን፣ ቀዳማዊ ኃይለስላሴን፣ ንጉሥ ጦናን፣ አሉላ አባ ነጋን፣ በላይ ዘለቀን፣ ሱልጣን አሊሚራህን፣ አባ ጅፋርን፣ ጄኔራል ጀጋማ ኬሎን፣ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን፣ ባሮ ቱምሳን፣ ተስፋዬ ደበሳይን፣ አብርሃም ደቦጭን፣ አበበ አረጋይን፣ ሌንጮ ለታን፣ ጄኔራል ከማል ገልቹን፣ አንዳርጋቸው ጽጌን፣ እስክንድር ነጋን…ወዘተ እነዚህን ሁሉ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች በሰብዕናቸውና በኢትዮጵያዊነታቸው እንጂ በጎሳቸው፣ በቋንቋቸው  እየከፋፈለ  የሚያይ ሳያረጅ የጃጀ፣ እውቀት ሳይገበይ የሳተ፣ ያለዚያም የፖለቲካ ንግድ ፈቃድ አውጥቶ የሚሮጥ ሸፋጭ ነው።

ትችቴን አንድ የውጭ አገር ፀሃፊ የኢትዮጵያውያንን  ጨዋነት በገለጸበት ታሪክ ልደመድመው ወደድሁ። የጎደለን እውነተኝነትና ጨዋነት ስለሆነ። ጸሃፊው ኢትዮጵያ ከጣልያን ጋር ስትዋጋ ከጎኗ ተሰልፎ ብዙ መስዋዕት የከፈለውና ያየውንም እውነት የመሰከረው አዶልፍ ፓርለሳክ ነው። “የሃበሻ ጀብዱ” በሚለውና ተጫነ ጆብሬ መኮንን  በተረጎሙት ገጽ 111 ላይ እንዲህ ይቀርባል።

በአድዋ ጦርነት ጊዜ አምባላጌን ይዟት ለነበረው የጣልያን ሻለቃ ቶለሲን ራስ መኮንን እንዲህ ብለው ነበር።

“ውድ ወዳጄ ሻለቃ ቶለሲ፤ ጀግንነትህንና ቆራጥነትህን አውቃለሁና አከብርሃለሁ። አደንቅሃለሁ።ይሁን እንጂ በዚህ ጦርነት ትሸነፋለህ። ስለዚህ አምባላጌን ለቅቀህ ወደ መቀሌ ሽሽ። እንዲህ በሰላም አምባላጌን ለቅቀህ ከወጣህ ጦርህ እንደታጠቀ ወደ መቀሌ ሸሽቶ ያለችግር እንደሚገባ ቃሌን እሰጥሃለሁ። ወዳጄ ቶለሲ ያለህን ጦር አውቃለሁ። እኔ አስር እጥፍ ጦር አለኝ። እና ኋላ በወታደሮቼ ብትገደል ልቤ ያዝናልና እባክህ አምባላጌን ለቅቀህ ውጣ።” ብለው መልዕክት ቢልኩበትም፣ ሻለቃ ቶለሲ “ከአለቆቼ ተጨማሪ ትዕዛዝ ካላገኘሁ አምባላጌን መልቀቅ አልችልም” ብሎ የራስ መኮንን ልመና ባለመቀበሉ ራስ መኮንን ሁለተኛ ጊዜ ለሻለቃ ቶለሲ መልዕክት ሲልኩ እንዲህ ብለው ነበር።

“ነገ ማለዳ ጦሬ ይዘምትብሃል።አሁንም ደግሜ ላሳውቅህ። ጦርህን ይዘህ ሂድ። ልቤን አታሳዝነው።” ሻለቃ ቶለሲ በድጋሚ የራስ መኮንንን ደግነት ባለመቀበሉ የራስ መኮንን ጦር የሻለቃ ቶለሲን ጦር ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር አጨደው።

በኋላ ራስ መኮንን የሻለቃ ቶለሲን ሬሳ አስፈልገው ወታደሮቻቸውን ለአንድ ጀግና በሚገባው ክብር እንዲቀበር አዘው ዐይናቸው ያዘለውን እንባ ለመዋጥ ሺጣጣሩ ታይተዋል። እንግዲህ እንዲህ ዓይነት የጦር መሪ ያፈራችውን ሃገር ነበር ጣልያኖች ዛሬም ያልሰለጠነች አረመኔ ሃገር አድርገው በመላው ዓለም ጉራቸውን የሚነፉት።”  ብሏል።

ከመቶ ዓመት በፊት በአድዋው ጦርነት አገርን ለወረረና ለተዋጋ ጠላት አባቶቻችን የሰጡትን ክብር እንኳ ለመሰል ዜጋችን መስጠት ሲሳነን የሚያሳዝን ነው። ለዚህ ፈረንጅ የኢትዮጵያውያንን ጨዋነት ለማወቅና ለመመስከር ኢትዮጵያዊ ሆኖ መወለድ ሆነ ማደግ አላስፈለገውም። ንፁህ ህሊናና ብሩህ አዕምሮ ብቻ ነው የሚጠይቀው። ህሊናችን በአድርባይነት፣ በምቀኝነት፣ በንዋይና በስልጣን ስስት ከጨቀየ የምንናገረውና የምናደርገው ሁሉ አገርና ህዝብን መጉዳቱ አይቀርም። መልካም ዛፍ በፍሬው ይታወቃልና ከምንናገረው የበለጠ የምናደርገው በማንነታችን ላይ ምስክር ሆኖ የኖራል።

አገራችን መስቀለኛ መንገድ ላይ ናት። አደገኛ አጥፊዋም በስልጣን ላይ ያለው ዘረኛ አምባገነን ስርዓት ነው። የትግሉ አቅጣጫ ሁሉ ስርዓቱን ለመቀየር  ተባብሮ በመታገል የሁሉም የሆነች ኢትዮጵያን መገምባት ሊሆን ይገባል። በጎንዮሽ ጦር እየሰበቁ ወገንን ለመውጋት ጊዜና ጉልበት ማባከኑ ቢያበቃ መልካም ነው። ድክመቶችም ካሉ በጨዋነት እየተመካከሩ ማረም ከኪሳራው ትርፉ ያመዝናል። ፕሮፌሰር መስፍንን ጭቃ ላይ ለመጎተት ህሊና ያልዳኛቸውን ዛሬ ስለሚሉትና ነገ ስለሚያደርጉት እንዴት እንመናቸ? በመተሳሰብና በመመካከር ወደጋራ የአገር ጥላት ማተኮር ይሻላል በማለት ቁጭቴን ለመግለጽ በመሆኑ ሃሳቤ የሚያስቀይማችሁ ካላችሁ አስቀድሜ ይቅርታ እጠይቃለሁ። ከተሳሳትሁም ለመታረም ዝግጁ ነኝ።

ቸር እንሰንብት

ኢትዮጵያን ተባብረንና ተከባብረን ካጥፊዎቿ እናድናት

ጸሃፊውን በ amerid2000@gmail.com ማግኘት ይቻላል

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የ24 ሰዓት የተቃውሞ ሰልፍ ጠራ

$
0
0

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የመጀመሪያ ዙር ህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ይፋ አደረገ

• የ24 ሰዓት (የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ ተጠርቷል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡
yilikal getenet
‹‹ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ›› እንዳዘጋጀ ያሳወቀው ትብብሩ የትግሉ ዓላማ ፍትሃዊ ምርጫ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጾአል፡፡

‹‹ምርጫ ቦርድ ለገዥው ፓርቲ ያለውን ወገናዊነትና ጉዳይ አስፈጻሚነት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል›› ያለው መግለጫው በመጀመሪያ ዙር የአንድ ወር ፕሮግራሙ 6 ዋና ዋና ተግባራትን ለመፈጸም ዝርዝር እቅዶችን አውጥቶ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡ በህዳር ወር የሚያከናውናቸው ተግባራትም፡-

1. በቤተ እምነት ጸሎት እንዲደረግና ጥሪ ማቅረብና አማኞች እንደየ እምነታቸው ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማድረግ
2. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ
3. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት (ሰላማዊ ሰልፍ)
4. ለመንግስት ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት
5. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግና
6. የህዝብን ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ እንደሆኑ በመግለጫው አሳውቋል፡፡

ከእቅዶቹ መካከልም በሶስት ተከታታይ እሁዶች በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች 3 የአደባባይ ስብሰባዎች እንደሚኖሩ፣ በመጨረሻው መርሃ ግብርም ህዳር 27ና 28 በፕሮግራሙ ማጠቃለያነት የ24 ሰዓት (የውሎና የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚደረግ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ገልጸዋል፡፡

በገዥው ፓርቲና በምርጫ ቦርድ ጥምረት ይፈጸማል ያለውን ህገ ወጥ ተግባር በመታገል ለሰላማዊ ትግሉ አወንታዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት እስከመጨረሻው በፅናት ለመቆም መዘጋጀቱን የገለጸው ትብብሩ በአገር ቤትና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ በትብብሩ ሂደት ቆይተው እስካሁን ያልፈረሙና ሌሎች ፓርቲዎች እና የዓለም አቀፉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡

በስብሰባ ጋጋታ የተማረውን ሕብረተሰ የሸፈተ ልብ ምርኮኛ ማድረግ አይቻልም

$
0
0

Teachers Unionበሰደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ ከተቋቋመበት ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ  በትምህርት ሥርዓቱ ላይ ያጋጠመውን ዙሪያ ገብ ችግር ፣ በመምህራን ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና በደል ከዚህ አንፃር መምህራን የትምህርቱን ጥራት ለማስጠበቅና መብቶቻቸውን ለማስከበር ማድረግ ያለባቸውን  እንቅስቃሴና መወሰድ የሚገባቸውን እርምጃ በተመለከተ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ መግለጫዎችን በማውጣት  በ መላው ዓለም ላሉ ኢትዮጵያውያን ባጠቃላይና በተለይ ለጉዳዩ ባለቤቶች ለኢትዮያጵያ መምህራን ፣  ለተማሪዎችና ለወላጆች እንዲደርስ አድርጓል።

[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

 

 

የግንቦት 7 ወቅታዊ ጽሁፍ: የወያኔ ግፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ

$
0
0

Ginbot-7-Top-logo_4
ዘረኛዉ ወያኔና ባለሟሎቹ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላና በሸኮ መዠንገር አካባቢ የሚያካሄዱትን የማንአለብኝነት የመሬት ዝርፍያና ዜጎችን እርስ በርስ በማጋጨት ተጠቃሚ ለመሆን የሚያደርጉት አራዊታዊ ሩጫ የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ህዝብ ይህ ነዉ ተብሎ ሊነገር የማይችል እልቂት እየተፈጸመበት ነዉ። የመዠንገር ህዝብ የሞትና የህይወትን ያክል የማይወጣዉ ምርጫ ስለቀረበለት ተወልዶ ያደገበትን የአባቶቹንና የአያቶቹን አካባቢ ለቅቆ በመዉጣት እራሱን ለመከላከል ባደረገዉ እንቅስቃሴ የብዙ ንጹሃን ዜጎችና ቁጥራቸዉ ቀላል የማይባል ምስኪን ወታደሮችም ህይወት ማለፉ በይፋ እየተሰማ ነዉ። ይህንን ተከትሎ ግፈኞቹ የወያኔ መሪዎች በአካባቢዉ ብዙ ዘመን በቆዩ ብሄሰቦች መካክል ሆን ብለዉ ግጭት እንዲነሳ እያደረጉ በህዝብ መካክል ግጭትትና ዕልቂት የተነሳ በማስመሰል በአካባቢዉ ከፍተኛ ሰቆቃ በመፈፀም ላይ ይገኛሉ።

በዚህ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች እየደረሰ ላለዉ መጠነ ሰፊ ግጭትና ዕልቂት ተጠያቂዉ በአካባቢዉ ለዘመናት አብሮ በመደጋገፍ የኖረዉ ህዝብ ሳይሆን የዚህ አሰቃቂ ዕልቂት ባለቤትና ጠንሳሽ ህወሓትና ዘረኛ መሪዎቹ መሆናቸዉን ለአንድም ደቂቃ ሊዘነጋ አይገባም። ይህ ግጭት ሊነሳ የቻለዉ ህወሓት የአካባቢዉን ደሃ ገበሬ ከትዉልድ መሬቱ ላይ እያፈናቀለ መሬቱን ለከፍተኛ የጦር መኮንኖቹና የኔ ለሚላቸዉ ባለሟሎቹ በማከፋፈሉ መሆኑን ይህንን ግፍ የሚሰማ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ልብ ሊለዉ ይገባል። ህወሃት የአማራን ተወላጆች አካባቢዉ የእናንተ አይደለምና ዉጡ እያለና እያፈናቀለ በሌላ በኩል ግን በየክልሉ የአካባቢዉን ነዋሪ እያፈናቀለ የራሱን ሰዎች የመሬት ባለቤት ማድረጉ አዲስ የጀመረዉ ክስተት ሳይሆን ቆየት ያለና ስር የሰደደ የወያኔ አሰራር ነዉ።

ይህ ዛሬ በጋምቤላና በአካባቢዋ እየደረሰ ያለዉ ግፍና መከራ ለአካባቢዉ ህዝብ ብቻ የሚተዉ ነጠላ ችግር ሳይሆን በአጠቃላይ ወያኔ በአገራችን ላይ ሆን ብሎ በማድረስ ላይ ያለዉ ችግርና መከራ አካል ነዉ። በጋምቤላ ዉስጥ የፈሰሰዉና እየፈሰሰ ያለዉ የሴቶች፤ የወጣቶች፤ የአረጋዉያንና የህጸናት ደም ለሁላችንም የነጻነት ጥሪ እያቀረበልን ነዉ። ይህ የነጻነት ጥሪ ሰምተን የምናልፈዉ ወይም ነገ እንደርሳለን በለን በቀጠሮ የምናልፈዉ ጥሪ አይደለም። ጥያቄዉ የአገርና የዜጎች ህልዉና ጥያቄ ነዉና ነገ ዛሬ ሳንል አሁኑኑ ይህንን የነጸነት ጥሪ ሰምተን ምላሽ ልንሰጠዉ ይገባል።
ginbot 7
ይህ ወያኔ በደቡብ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ዉስጥ በንጹሃን ዜጎቻችን ህይወት ላይ እየፈጸመ ያለዉ ግፍ በአገራችን ህዝብ ላይ ሲደርስ የመጀመሪያዉ አይደለም፤ ካላቆምነዉ በቀር የመጨረሻዉ እንደማይሆንም አካሄዱ በግልጽ እያሳየን ነዉ። ወያኔ ጋምቤላ ዉስጥ ለምለም መሬት እየፈለገና ነዋሪዉን እያፈናቀለ መሬቱን ለባለሟሎቹ ማደሉን ሳይታቀብ በማንለብኝነት እንደቀጠለበት ነዉ። መሬቱን የተቀማዉ ደሃዉ የጋምቤላ ገበሬም ጫካ እየገባ ከወያኔ ጋር መተናነቁን ቀጥሏል። ትናንት በኦሮሚያ፤ በጉራፈርዳና በቤንሻንጉል አካባቢዎች በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰዉ ግፍና መከራ ዛሬ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተለያዩ ብሄረሰቦች ላይ እየደረሰ ነዉ።

ግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ እንቅስቃሴ ይህ ለከቱን የለቀቀ የህወሓት ዕብሪት እንዲተነፍስና በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰዉ ግፍና ሰቆቃ እንዲቆም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ነግ በኔ እያለ የነጻነት ትግሉን እንደቀላቀል የትግል ጥሪ ያደርጋል። ወያኔ እያደረሰ ያለዉ እስራት፤ ድብደባ፤ ግድያና ስደት የሁላችንንም ቤት እያንኳኳ ነዉና ሁላችንም እንደ አንድ ሰዉ ቆመን ወያኔንና ወያኔ የፈጠረዉን ዘረኛ ስርዐት በትግላችን መደምሰስ አለብን። በጋምቤላና በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች የፈሰሰዉ የንጹሃን ወገኖቻችን ደም ደመከልብ ሆኖ የማይቀረዉ ለመብታችንና ለነጻነታችን ቆመን ወያኔን ካስወገድን ብቻ ነዉ።

በህብረት እንነሳ!!!!

Sport: አንድሬስ ኢንዬሽታ –የዘመኑ የእግር ኳስ ቴክኒሽያን

$
0
0

ወደ ባርሴሎናው ካምፕኑ ያመራ ዕድለኛ የሆነ ሰው ሁሉ አንድ ነገር ያስተውላል፡፡ ‹‹Mesque un lcub›› የሚሉትን ቃላት፡፡ ‹‹ከክለብም በላይ!›› ይህ መፈክር የካታላኑን ክለብ ፍልስፍና የሁሉም አቅጣጫዎች በአንድ ላይ ሰብስቦ የሚይዝ ነው፡፡ አሁን በክለቡ ያለው የከዋክብት ስብስብ ይህን የባርሴሎናን ስሜት የሚወክል ነው፡፡ ፍልስፍናውን በኩራት ከሚወክሉት ተጨዋቾች መካከል በመጀመሪያዎቹ ረድፍ የሚቀመጠው ደግሞ አንድ ሰው ነው፡፡ አንድሬስ ኢንዬሽታ፡፡
inesta
እርሱን ስትመለከቱት ወደ ጭንቅላታችሁ የሚመጣው ምስል ላለፉት 10 ዓመታት እግርኳስን ውብ ያደረገ ተጨዋች ላይሆን ይችላል፡፡ የቁመቱ ማጠር እና በኋለኛው ክፍለ ዘመን ከአንድ አትሌት የሚጠበቁት ፍጥነት እና ኃይል የሌለው መሆኑ በእግር ኳስ ሜዳ ላይ ጎልቶ ከመውጣት አላገዱትም፡፡ በዚህ ያጣውን ነገር ባለው የላቀ የቴክኒክ ተሰጥኦ ያካክሰዋል፡፡ ላለፉት ዓመታት ከጎኑ ካልጠፋው ዣቪ ሄርናንዴዝ ጋር በመሆን ተጋጣሚዎቻቸውን አስገብረዋል፡፡ ኢኒዬሽታ ባለው የፈጠራ እይታ እና የኳስ ማቀበል ችሎታ ኑ ካምፕን አድምቋል፡፡ የ30 ዓመቱ ተጨዋች በዘመናዊው እግርኳስ ባላቀ የመሀል ሜዳ አማካይነት ስኬታማ ለመሆን የሚያስፈልገው ምን እንደሆነ ላለፉት 10 ዓመታት በብቃት አሳይቷል፡፡ ጨዋታን በመቆጣጠር ታላቁ የባርሴሎና ቡድን የዓለም ኃያል እንዲሆን አስችሎታል፡፡

እግርኳስ ውብ ጨዋታ ነው፡፡ ኢኒዬሽታ ደግሞ የእግርኳስ ውበት ምልክት ነው፡፡ የቦታ አያያዙ ከማንም ያነሰ አይደለም፡፡ ጨዋታን የማንበብ ብቃቱ በተአምራዊ የእግሮቹ ጥበብ ሲታገዝ ለማየት ያጓጓል፡፡ በእርግጥ አብዛኛው የእግርኳስ ደጋፊ የኢኒዬሽታን ብቃት መታዘብ የቻለው ከ2009 ወዲህ ቢሆንም የአማካይ ክፍሉ አርቲስት ግን ከ2002 ጀምሮ የኑካምፕ ደጋፊዎችን ልብ ሀሴት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በወቅቱ የ18 ዓመት አማካይ የባርሳን የዋናውን ቡድን ማልያ ለመጀመሪያ ጊዜ የለበሱት ልዊስ ቫን ሃል ናቸው፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ በላ ማሲያ ያደረገው ኢኒዬሽታን ለብሉ ግራንስ የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደረገው በቻምፒዮንስ ሊጉ ቡድን ክለብ ብሩዥን ሲገጥም ነበር፡፡ ከባርሴሎና ቢ ቡድን ጋር ሲጫወት የነበረው ወጣቱ ኢኒዬሽታን በመጀመሪያ የውድድር ዘመኑ ተፅዕኖው ከፍ ያለ ነበር፡፡ ሆኖም የካታላኑን ቡድን የሚከታተሉ ሁሉ ልጁ እምቅ ችሎታ እንዳለው ታዝበዋል፡፡

በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት ኢኒዬሽታ በባርሴሎና ወሳኝ ሚና እያደረገ መጥቷል፡፡ በ2004/05 በፍራንክ ራይካርድ ስር በላሊጋው በ37 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫወተ፡፡ ምንም እንኳን አብዛኛዎቹን ጨዋታዎች ከተጠባባቂ ወንበር እየተነሳ ቢሳተፍም በወቅቱ ላበረከተው አስተዋፅኦ ኩራት ተሰምቶታል፡፡ በዚያ የውድድር ዘመን ባርሴሎና ከ1999 ወዲህ የመጀመሪያ የሊግ ዋንጫን አግኝቷል፡፡ በቀጣዩ የውድድር ዘመን በ2005/06 ዣቪ ያጋጠመው ጉዳት ኢኒዬሽታ ብዙ ጨዋታዎችን እንዲያደርግ አስቻለው፡፡ በሊግ የውድድር ዘመንም ባርሴሎና የላሊጋ ሻምፒዮንነቱን በድጋሚ አስከበረ፡፡ ሆኖም ደጋፊዎቹ ዣቪ እና ኢኒዬሽታ አንድ ላይ መጫወት እንደማይችሉ ማሰብ ጀመሩ፡፡ ሆኖም በ2006 የቻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ሁለቱ ተጨዋቾች ተጠባባቂ ሆኑ፡፡ ራይካርድ አርሰናል በሜዳው የመሀል ክፍል ያለውን አካላዊ ጥንካሬ ለመግታት የኤድሚልሰን፣ ዴኮ እና ማርክ ቫን በሜልን ጥምረት ተጠቀመ፡፡

ሆኖም ኢኒዬሽታ የተጎዳውን ኤድሚልሰን በእረፍት ሰዓት ቀይሮ ገባ፡፡ ሳሙኤል ኤቶ ያስቆጠራት የአቻነት ጎል መነሻም የኢኒዬሽታ ችግሮች ነበሩ፡፡ ባርሴሎና ጨዋታውን 2-1 አሸነፈ፡፡ ውጤቱ ቡድኑን የአውሮፓ እግርኳስ ቁንጮ አደረገው፡፡ ከዚያ በኋላ ክለቡ የእግርኳስ ፍልስፍናን መሰረት የጣለው በዚያ ቡድን መነሻነት ነው፡፡ ራይካርድ የራሱ ስኬት ተጎጂ ሆነ፡፡ በ2008 ባርሴሎና አንድም ዋንጫ አለማሸነፉን ተከትሎ ራይካርድ ከአሰልጣኝነቱ ተሰናበተ፡፡ ለፔፕ ጋርዲዮላም በር ከፈተለት፡፡ አዲሱ የቲካታካ ዘመንም ተጀመረ፡፡

ሞዴሉ ጋርዲዮላ ከመምጣቱም በፊት የባርሴሎና ፍልስፍና የልብ ምት ነበር፡፡ የኳስ ቁጥጥር እና አጭር ቅብብል ከታዳጊዎቹ ጀምሮ እስከ ዋናው ቡድን ድረስ የአጨዋወት መንገዶች ናቸው፡፡ ፔፕ ከመጣ በኋላ የካታላኑ ክለብ በዓለም እግርኳስ ተከታታዮች ልብ ውስጥ ገባ፡፡ ባርሴሎና እና ኢኒዬሽታም የታላቅነት ማማ ላይ ወጡ፡፡ የ2008/09 ከምንጊዜውም ምርጥ ቡድኖች የመጀመሪያውን ረድፍ ላይ የሚቀመጥ ቡድን ሆነ፡፡ የጋርዲዮላ የመጀመሪያው የውድድር ዘመን አይረሴ ነበር፡፡ ገና የውድድር ዘመኑ ሳይጀመር የኮከብ ሮናልዶንም መልቀቅ ቡድኑን እንዳልነበር ያደርገዋል የሚል ከፍተኛ ግምት ነበር፡፡ በምት ግን ሊዮኔል ሜሲ የዓለም ታላቅ ተጨዋች ሆኖ ብቅ አለ፡፡ ትንሹ አርጀንቲናዊ ከባለ ተሰጥኦ ከዋክብት አንዱ የነበረ ቢሆንም የተደረገለት የቦታ ለውጥ ከፍ ያለ ነፃነት አስገኝቶለት ብቃቱ ወደ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋገረ፡፡ ባርሴሎናም በዚያ የውድድር ዘመን የላ ሊጋውን ያለ ችግር አሸነፈ፡፡ ሜሲ በሊጉ 23 ጎሎችን አስቆጠረ፡፡ በኮፓ ዴል ሬይ ስድስት ተጨማሪ ጎሎችን አስቆጠረ፡፡ የካታላኑ ክለብ የሀገር ውስጥ ሁለት ዋንጫዎችን አገኙ፡፡

ለባርሴሎና ስኬት የትንሹ ጥበበኛ አስተዋፅኦ ከፍ ያለ መሆኑ አይጠረጠርም፡፡ ያለ እርሱ ባርሴሎና እዚህ ደረጃ ለመድረስ ይቸገር ነበር፡፡ ሆኖም የኢኒዬሽታ ዋጋም ያነ አይደለም፡፡ አማካዩ ጨዋታዎችን በመቆጣጠር ብሉ ግራንሰን ለክብር መርቷል፡፡ ኢኒዬሽታ በ2008/09 ለሁለት ወራት በጉዳት ምክንያት ከሜዳ ርቆ ነበር፡፡ ሆኖም ወደ ሜዳ ከተመለሰ በኋላ በኮፓ ዴል ሬይ እና በላሊጋው ስኬት ትልቅ ድርሻ ነበረው፤፤ የእርሱ ከፍተኛው አስተዋፅኦ የተገኘው ግን በቻምፒዮንስ ሊጉ ነው፡፡ በሀገር ውስጥ ከመጀመሪያ የውድድር ዘመኑ ሁለት ዋንጫ ማሸነፉ ለጋርዲዮላ ስኬት ይህን የተጨዋቾች ስብስብ ወደ ሌላ ዓለም ወሰደው፡፡ ነገር ግን የቻምፒዮንስ ሊጉ ግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ በስታምፎርድ ብሪጅ ሲደረግ ካታላናዊያኑ ከውድድሩ ለመውጣት ተቃርበው ነበር፡፡ ቼልሲ እስከ መጨረሻው ደቂቃ ድረስ በድምበር ውጤት ለፍፃሜ የሚያደርገውን ደረጃ አግኝቶ ነበር፡፡
በጨዋታው የመጨረሻ ደቂቃ ግን ነገሮች ተገለባበጡ፡፡ ኢኒዬሽታ ለታላቅነት ተንደረደረ፡፡ አማካዩ የምርጥ ብቃት ባለቤት ቢሆንም በጎል አግቢነት አይታወቅም፡፡ ተጨዋቹ ይበልጥ የሚታወቀው ለጎን የተመቻቹ ኳሶችን በማቀበል ነው፡፡ በስታምፎርድ ብሪጅ ግን ይህ አልሆነም፡፡ ከፍፁም ቅጣት ምቱ በዚህ ላይ በግራ እግሩ አክርሮ የመታት ኳስ የፔተር ቼክ መረብ ላይ አረፈች፡፡ ስፔናዊው ከድጋፍ ሰጪነት ወደ ኮከብነት በአንድ ምሽት ተሸጋገረ፡፡ ጎሏ በቻምፒዮንስ ሊጉ አይረሴ ከሆኑት ጎሎች መካከል አንዷ ሆነች፡፡ ባርሳም ለቻምፒዮንስ ሊጉ ፍፃሜ ደረሰ፡፡ አንድሬስም በካታላዊያን ልብ ውስጥ ላይፋቅ ተቀመጠ፡፡
ከሜሲ የፍፁም ቅጣት ምት ክልሉ ጫፍ ላይ ተቀበለ፡፡ ማድረግ ያሰበው አንድ ነገር ብቻ ነው፡፡ ወደ ግብ መምታት፡፡ እንደ እርሱ አይነት ሙከራ አድርገው የሚሳካላቸው ጥቂት ተጨዋቾች ብቻ ናቸው፡፡ ሙከራው ተሳካለት፡፡ ስታምፎርድ ብሪጅ በፀጥታ ተሞላ፡፡ ስታምፎርድ ብሪጅ በፀጥታ ተሞላ፡፡ የስታዲየሙ አንድ ክፍል ግን ከፍተኛ ጩኸት ይሰማበታል፡፡ የባርሳ ደጋፊዎች የሚይዙትን የሚጨብጡትን አጡ፡፡ ካታላናዊያንም ወደ ሮሙ ፍፃሜ አመሩ፡፡ በፍፃሜው ግጥሚያ ኢኒዬሽታ ወደ ተለመደ ሚናው ተመለሰ፡፡ ማንቸስተር ዩናይትድን 2-0 ባሸፉበት ጨዋታ ሳሙኤል ኤቶ ላስቆጠራት የመጀመሪያ ጎል ምርጥ ኳስ አቀብሏል፡፡ ምርጥ ብቃት ካሳየበት የውድድር ዘመን በኋላ በመላው ዓለም እውቅናን ማግኘት ጀመረ፡፡ ደጋፊዎች እና ሌሎች ተጨዋቾች አንድሬስ የምርጥነት ምልክት መሆኑን በተደጋጋሚ ተናገሩ፡፡

የስፔኑ ክለብ የቻምፒዮንስ ሊግን ዋንጫ በማንሳት በአንድ የውድድር ዘመን ሶስት ትልልቅ ክብሮችን ሲያሸንፍ ኢኒዬሽታ ወሳኝ ተጨዋች ነበር፡፡ በዚያ የውድድር ዘመን የላ ሊጋው ምር የሀገር ውስጥ ተጨዋች ተብሎ ተመረጠ፡፡ የላ ሊጋው ምርጥ ሌይሜከርነትንም ማዕረግ ተጎናፀፈ፡፡ ባርሴሎና በጋርዲዮላ ስር ኃያልነቱን ቀጠለ፡፡ ሀለት የሊግ ዋንጫዎች፣ የኮፓ ዴል ሬይ ክብር፣ ሌላ የቻምፒዮንስ ሊግ ማዕረግ እና ሁለት የዓለም ሻምፒዮንነትን ተቀዳጀ፡፡ ኢኒዬሽታም የዚህ የእግርኳስ ኃያልነት ዘመን አቀጣጣዮች አንዱ ሆኖ ቀጠለ፡፡ ከዓለም ምርጥ አማካዮች አንዱ መሆኑንም አስመሰከረ፡፡ ምንም እንኳን ከግብ ፊት ያሉ ሪከርዶችን ሁሉ የሰባበረው ሜሲ በግሉ በርካታ ሽማቶች ቢሰበስብም ለባርሴሎና ስኬት ኢኒዬሽታ የነበረውን አስተዋፅኦ ማንም አይጠራጠርም፡፡ ያለ ምርጡ አማካይ አጥቂው ሜሲ አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ ለመድረስ በመጠኑም ቢሆን ሊቸግር ይችል ነበር፡፡ አርጀንቲናዊው ኮከብም ቢሆን የስፔኑን ውለታ አይረሳም፡፡ እንዲያውም ሜሲ ያለ ኢኒዬሽታ እና ጓደኞቹ ድጋፍ ትልቅ ደረጃ ለመድረስ ይቸገር እንደነበር አምኗል፡፡ ምንም እንኳን የኢኒዬሽታ የባርሴሎና ኮከብ ተጨዋችነት ለክርክር የሚቀርብ ቢሆንም የክለቡን በዋንጫ የተሞላ ዓመታት መሪ ከሆኑት ተጨዋቾች መካከል አንዱ ነው፡፡

በሀገር ደረጃም ቢሆን ስፔን ከ2008 እስከ 2012 ድረስ ያስመዘገባቸው ስኬት በኢንተርናሽል ደረጃ የሚስተካከለው የለም፡፡ ከአልባሴቴ የተገኘው ኢኒዬሽታ ደግሞ ለቡድኑ ስኬት ቁልፍ ከነበሩ ተጨዋቾች አንዱ ነው፡፡ የኢኒዬሽታ የብሔራዊ ቡድን ስኬት የተጀመረው ግን ከዩሮ 2008 ድል በፊት ነው፡፡ የላ ሮያ ወጣት ቡድኖችን በ2001 እና 2002 ለድል መርቷል፡፡ ወደዋናው ቡድን እስኪጠራ ድረስም ከ21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኑን በተለያዩ አጋጣሚዎች በአምበልነት መርቷል፡፡ በዋናው ቡድን ምርጥነቱን ያሳየው ግን በዩሮ 2008 ነው፡፡ በኦስትሪያ እና ስዊዘርላንድ በተዘጋጀው የአውሮፓ ዋንጫ በተከታታይ ጨዋታዎች ድንቅ ብቃቱን ማሳየት ችሏል፡፡ በመድረኩ ያሳየው ብቃት በውድድሩ ምርጥ ቡድን ውስጥ እንዲካተት አስችሎታል፡፡ ከሁሉም በላይ ግን ስፔን ከ1964 ወዲህ ትልቅ ዋንጫን እንድታገኝ ቡድኑን በሚገባ ረድቷል፡፡ 2008 ደግሞ የስፔን ዓለም አቀፍ የበላይነት መጀመሪያ ነው፡፡

2010 ሌላው የኢኒዬሽታ እና ስፔን የስኬት ዓመት ነው፡፡ በደቡብ አፍሪካ የዓለም ዋንጫ ቡድኑ ለሻምፒዮንነት ተገምቶ ነበር፡፡ ሆኖም ለ6 ቁጥር ለባሹ ዓመቱ በሜዳ ላይም ሆነ ውጪ የተቸገረበት ዓመት ነበር፡፡ በውድድር ዘመኑ ያጋጠመው ጉዳት ግን በባርሴሎና የተጫወተባቸውን ጨዋታዎች ቁጥር ከመቀነሱም በላይ በዓለም እግርኳስ ትልቁ ውድድር ላይም ላይሳተፍበት የሚችል ዕድል ሰፋ፡፡ ጉቱ ከቪሴንቴ ዴል ቦስኬ ባሉ 23 ተጨዋቾች ስኳድ ውጪ ሊያደርገው ተቃርቦ ነበር፡፡ ከጉዳቱ በተጨማሪ ከሜዳ ውጪ ልብን የሚሰብር ነገር ገጥሞታል፡፡ የአማካይ ክፍሉ ድንቅ ተጨዋች በ2009/10 የውድድር ዘመን ሊጀመር ሲል የልጅነት ጓደኛውን ዳኒኤል ሀርኬን በሞት ተነጠቀ፡፡ በኦገስት 2009 የኤስፓኞል አምበል የነበረው ዳኒኤል ባጋጠመው የልብ ህመም ህይወቱ አለፈ፡፡ ጉዳዩን ይበልጥ አሳዛኝ የሚያደርገው ደግሞ ተጨዋቹ ህይወቱ ያለፈው ኤስፓኞል በጣልያን የቅድመ ውድድር ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅት ነበር፡፡ ዳኒኤል በወቅቱ 26 ዓመቱ ነበር፡፡

ኢኒዬሽታን ሀዘን ጎዳው፡፡ የባርሴሎናውን ኮከብ በቅርብ የሚያውቁት ሁሉ የጓደኛው ሞት ምን ያህል እንደጎዳው ታዝበዋል፡፡ ሆኖም የውድድር ዘመኑ መጨረሻ ላይ ዕድል ከተጫዋቹ ጋር ነበረች፡፡ በፍፃሜው ግጥሚያ ሆላንድ ላይ ጎል ካስቆጠረ በኋላ ኢኒዬሽታ ማሊያውን አወለቀ፡፡ በውስጥ በለበሰው ቲሸርት የሀርኬ ምስል ታትሞ ነበር፡፡ መላው ዓለም ጨዋታውን የተከታተለ ሁሉ ይህን ምስል አይረሱትም፡፡ የዓለም መገናኛ ብዙሃንም ምስሉን ተቀባበሉት፡፡ አንድሬስም የልጅነት ጓደኛውን በሚገባ አስታወሰ፡፡ የሟቹ ጓደኛው ፎቶ ምን ጊዜም ከስፔን ታላቅ ስኬት ጋር መገናኛት ችሏል፡፡

ስፔን በዓለም አቀፍ እግርኳስ የላይኛው ጫፍ ላይ እንደምትገኝ የ2012ቱን የአውሮፓ ዋንጫ በማሳየት አነሳች፡፡ በድጋሚ ኢኒዬሽታ ምርጥ ብቃቱን በማሳየት የውድድሩ ምርጥ ቡድን ውስጥ ከመካተት አልፎ የቶርናመንቱ ምርጥ ተጨዋችነትን ማዕረግ አገኘ፡፡ ኳስን ተቆጣጥሮ ማቆየት እና ለጎን የተመቻቹ ኳሶችን የማቀበል ችሎታው ከማንም ልቆ መታየት ቻለ፡፡ ምንም እንኳን በብራዚሉ የዓለም ዋንጫ ስፔን ሳይጠበቅ የመጀመሪያዎቹን ሁለት ጨዋታዎች ተሸንፋ ከምድቧ ሳታልፍ ብትቀርም ይህ ልዩ ቡድን የራሱን ገድል በታሪክ ድርሳናት ላይ ማስፈር የቻለ ነው፡፡ ከአልነሴቴ የተገኘው ልጅ ደግሞ የስኬቱ ምልክት ነው፡፡ በመጪዎቹ ዓመታት ከ2008 እስከ 2012 ያሉትን ዓመታት የሰፔን እግርኳስ ወርቃማ ዘመናት በማለት ደጋፊዎች ማክበራቸው አይቀርም፡፡ ይህ ወርቃማ ዘመን ሲነሳ ደግሞ የአኒዬሽታ ስም በድምቀት መዘከሩ አይቀሬ ነው፡፡ ባርሳን በ12 ዓመቱ የተቀላቀለው ልጅም ወደ ታላቅነት ተለውጧል፡፡

Health: ‹‹በእንቅልፍ ማጣት የዕለት ተዕለት ሕይወቴ ደስታ ርቆታል›› ጥያቄና የሕክምናው ምላሾች

$
0
0

ተከታታይ የሆነ የእንቅልፍ ማጣት ችግር አለብኝ፡፡ በዚህ ምክንያት የዕለት ተዕለት ህይወቴ የተመሰቃቀለና ደስታ የራቀው ሆኖብኛል፡፡ ከዚህም በላይ ከሰዎች ጋር የሚኖረኝ ግንኙነት በድብርት የተሞላ ነው፡፡ በሥራ አካባቢም በጣም ውጤታማ መሆን አልቻልኩም፡፡ ለመሆኑ እንቅልፍ ማጣት ከምን ይመነጫል? ህክምናውስ ምን ይመስላል? በጥቅሉ የእንቅልፍ ማጣት ችግሬን እንዴት ላቃልል እችላለሁ?
አቤኔዘር የሻው ነኝ

ከአዘጋጁ፡-
ውድ ጠያቂያችን እንቅልፍ ማጣት የብዙ ሰዎች ችግር ነው፡፡ ዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈሮ በድረገፃቸው ካሰፈሩት መረጃና በችግሩ ዙሪያ ጥናት ያደረጉ የህክምና ባለሙያዎች በድረገፅ ያሰፈሯቸውን መረጃዎች ተንተርሰን የሚከተለውን ምላሽ ሰጥተንሃል፡፡
ዶ/ር ሆነሊያት እንደሚሉት በቂ እንቅልፍ ካላገኘን የመነጫነጭ፣ ለሥራ ተነሳሽነት ማጣት፣ ድካም የመሳሰሉት ይከሰታሉ፡፡ ከእነዚህ ቀላል ከሚባሉ የዕለት ተዕለት ባህሪ ለውጦች በተጨማሪ የእንቅልፍ እጦት ከፍተኛ የጤና ችግሮችን ያከስትላል፡፡
1. የእንቅልፍ እጦት ለሚከተሉት የጤና ችግሮች መንስኤ ሊሆን ይችላል፡፡ ለልብ ህመም፣ ለደም ግፊት፣ ለስትሮክ፣ ለስኳር ህመም፡፡
sleep disorder2. የመደበት ስሜትን ያስከትላል
የተለያዩ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ከሆነ ለረጅም ጊዜ በእንቅልፍ እጦት የሚሰቃዩ ሰዎች የመደበት ስሜት ያጠቃቸዋል፡፡ ይጫጫናቸዋል፣ ያፋሽካሉ፣ አይናቸው ይቀላል በአጠቃላይ በድብርት የተሞሉ ናቸው፡፡
3. የሰውነት ክብደት መጨመር
የእንቅልፍ እጦት የረሃብ ስሜት ቀስቃሽ የሆኑ ሆርሞኖችን በሰውነታችን እንዲመነጩ ስለሚያደርግና ከፍተኛ የምግብ ፍላጎት እንዲኖረን ስለሚያደርግ የሰውነት ክብደታችን እንዲጨምር ያደርጋል፡፡
4.ቆዳችን ያለ ዕድሜ እንዲሸበሸብ ምክንያት ይሆናል
የእንቅልፍ ማጣትን ተከትሎ የሚታየው የአይን ማበጥና መቅላት እንዳለ ሆኖ ከዚህ ባለፈ በዓይን አካባቢ ጥቁር የሆኑ ቀጭን መስመሮችና የቆዳ መሸብሸብ የእንቅልፍ እጦት ከሚያስከትላቸውና በቆዳ ላይ ከሚታዩ ችግሮች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
5. ውጤታማነትን ይቀንሳል
በቂ እንቅልፍ የማያገኝ ሰው ማንኛውንም ስራ ለመተግበር አቅም ስለማይኖረውና የሥራ ፍላጎቱ ስለሚቀንስ በሥራ ወቅት የሚፈጥራቸው ስህተቶች ጉልህ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ውጤታማነት በእጅጉ ይቀንሳል፡፡
6. ለአደጋ ያጋልጣል
እንደ አንዳንድ የጥናት ውጤቶች መረጃ የእንቅልፍ እጦት ለመንገድ ትራፊክ አደጋዎች፣ በስራ አካባቢ የሚደርሱ የማሽን አደጋዎችና በቸልተኝነት ለሚከሰቱ የእሳት አደጋዎች ከፍተኛውን ሚና ይጫወታል፡፡
እንቅልፍ የማጣት ስሜት እንዴት ይከሰታል?
በርካታ የህክምና ባለሙያዎች ባካሄዷቸው ጥናቶች እንቅልፍ የማጣት ስሜቶች በጊዜያዊና በተከታታይ የሚከሰቱ በሚል በሁለት ይከፍሏቸዋል፡፡
ጊዜያዊ የእንቅልፍ እጦት መንስኤዎች
– አነቃቂ (አደንዛዥ) እፆችን መጠቀም
– በእንቅልፍ ሰዓት እንደ ሻይ ቡና ጫት የመሳሰሉ አነቃቂ ነገሮችን መውሰድ
– ሃሳብና ጭንቀት በህይወታችን ውስጥ አንድ አልሳካ ያለ ጉዳይ ሲገጥመንና ጉዳዩ ከባድ ሐሳብ ሲያስከትል ለተደጋጋሚ ውጥረትና ጭንቀት ሊዳርግ ይችላል፡፡
– የመኝታ ስፍራ አለመመቸት
– አስፈሪ ፊልሞችን በምሽት መመልከት
– ሰላማዊና ፀጥታ የሰፈነበት ቦታ ካለመተኛትና ከመሳሰሉት ገጠመኞች ጊዜያዊ የእንቅልፍ እጦት ሊያስከትል ይችላል፡፡
በተከታታይ የሚከሰት የእንቅልፍ እጦት መንስኤዎች
አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያረጋግጡት ለተከታታይ ቀናት የእንቅልፍ ማጣት ችግሮች መንስኤዎቻቸው ውስብስብ ናቸው፡፡ እነዚህም እንየግለሰቡ ባህሪ የተለያዩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ በዋናነት ግን ብስጭት ይጠቀሳል፡፡ በህይወት ሂደት የሚገጥሙ መሰናክሎች አንዳንድ ጊዜ ረፍት ሊነሱና ጤናማ እንቅልፍ ሊያሳጡ ይችላሉ፡፡ ፍቅር ሲይዝ ይህ ሁኔታም ሊያጋጥም እንደሚችል አንዳንድ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ በፍቅር የተያዘ ወይም የተያዘች ሴት ለተከታታይ ቀናት እንቅልፍ እስከማጣት የደረሰ የስነ ልቦና ቀውስ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ፡፡

ውድ ጠያቂያችን
ለአጭር ጊዜ ወይም ለረዥም (ለተከታታይ ቀናት) የሚያጡት እንቅልፍ የሚያስከትላቸውን ጉዳቶች ቀደም ሲል ተመልክተናል፡፡ መንስኤዎቹንም አይተናል፡፡ በማስከተል ደግ የመፍትሄ ሃሳቦችን እንጠቁምህ፡፡

መፍትሄዎች

1. መኝታ ቦታን ምቹና ፅዱ ማድረግ
የመኝታ ክፍሎቻችን ፅዱና ማራኪ እንዲሆኑ ማድረግ ይገባል፡፡ ፍራሾችና ትራሶችም በተቻለ አቅም ምቹ እንዲሆኑ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ አንሶላዎቻችን መልካም መአዛ (ጠረን) እንዲኖራቸው ብንሞክርም አይከፋም፡፡
2. ተገቢውን ጊዜ መስጠት
አንድ ሰው በቀን ውስጥ ስምንት ሰዓታትን በእንቅልፍ ቢያሳልፍ ለጤናማ የእለት ተዕለት ህይወቱ ይመከራል፡፡ በመሆኑም ለእንቅልፍ ሰዓት ተገቢውን ጊዜ መስጠት ያሻል፡፡
3. ከአደንዛዥና አነቃቂ ዕፆች መላቀቅ
አንዳንድ ሰዎች በራሳቸው ችግር ለእንቅልፍ እጦት ይዳረጋሉ፡፡ ለምሳ በምሽት አነቃቂና አደንዛዥ ዕፆችን ከመጠቀም በመቆጠብ ጤናማ እንቅልፍ መተኛት እየቻሉ ልምድ (ሱስ) ሆኖባቸው ሲጠቀሙ ይስተዋላል፡፡
4. ሃሳብና ጭንቀትን ማቃለል፡-
ከአቅም በላይ ለሆኑ ጉዳዮች ብዙ አለመጨነቅ፡፡ ነገሮች እንዲሳኩ ተገቢውን ጥረት ከማድረግ ውጪ ከአቅም በላይ በሀሳብና ጭንቀት ራስን ከመጉዳት ይታቀቡ፡፡ ምክንያቱም ነገሮች ሁል ጊዜ በፈለግነው መልኩ ብቻ ሊሄዱ አይችሉምና፡፡

የእንቅልፍ መድሃኒት

ለተከታታይ ቀናት በእንቅልፍ እጦት የሚሰቃዩ ሰዎች የእንቅልፍ እንክብል (ክኒን) በመውሰድ እንቅልፍ ለመተኛት ሲሞክሩ ይስተዋላል፡፡ ይሁን እንጂ ይህን መንገድ የህክምና ባለሙያዎች አያበረታቱም፡፡ ምክንያቱም በመድሃኒቱ በመታገዝ የሚተኛው እንቅልፍ በተፈጥሮ የምንተኛውን ያህል አይሆንም፡፡ ከዚህም በላይ መድሃኒቱ የልብ ድካም ላለባቸው ሰዎች አይመከርም፡፡ ለማንኛውም ሰው የሰውነትን ሆርሞኖች ወይም ሴሎች የማዳከም ባህሪም አለው፡፡ ስለሆነም በተቻለ መጠን በተፈጥሮ ሰውነታችን የሚፈልገውን እረፍትና እንቅልፍ እንዲያገኝ ማድረግ ይገባል፡፡
ለረዥም ጊዜ በእንቅልፍ እጦት የሚሰቃይ ሰው ወደ ህክምና ተቋም በመሄድ ሐኪም በማማከር ተገቢውን የህክምና እርዳታ ማግኘት ይኖርበታል፡፡ እንጂ በራሱ የእንቅልፍ መድሃኒት ከመድሃኒት መደብሮች ገዝቶ ከመጠቀም እንዲታቀብ የህክምና ባለሙያዎች ይመክራሉ፡፡

ውድ ጠያቂያችን የዕለት ተዕለት ሕይወትህ በእንቅልፍ እጦት ከመመሰቃቀልና ደስታን ከማጣት የምትላቀቅባቸውን ጠቃሚ ሃሳቦች አካፍለናል፡፡ ከእንቅልፍ እጦት ጋር በተያያዘ በርካታ ቤተሰቦች ሲቸገሩ እናያለን፡፡ ከቤተሰብ አባላት መካከል አንድ ወይም ሁለት ሰዎች በእንቅልፍ እጦት ሲቸገሩ የሌሎችን የቤተሰብ አባላት ሰላማዊ እንቅልፍ ሲያውኩ ማየት የተለመደ ነው፡፡ በተለይም እናቶች ህፃናት ልጆቻቸው የእንቅልፍ እጦት ሲገጥማቸው አባብለው ለማስተኛት ሲቸገሩ ይስተዋላል፡፡ በመሆኑም ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለእናቶች ጠቃሚ ሃሳቦችን ለማካፈል ወደድን፡፡
በኖተርዳም ዩኒቨርሲቲ የሥነ ሕይወት ፕሮፌሰር የሆኑት ጀምስ ማክኪና ለህፃናት ሰላማዊና ጤናማ የእንቅልፍ አካባቢን ለመፍጠር የሚረዱ ሃሳቦችን እንደሚከተለው ያካፍላሉ፡፡
ለእናቶች
– ህጻናት በተለይም ጨቅላ ህፃናትን ከመተኛታቸው በፊት ለብ ባለ ውሃ በማጠብ የሌሊት ልብስ አልብሰውና ጡት በሚገባ አጥብተው ያስተኙ፡፡
– የህፃኑ መተኛ ስፍራ በቂ ሙቀት የሚስብ ይሁን
– የመኝታ አካባቢው ከጭስ ነፃ ይሁን
– ጨቅላው በጀርባው ተንጋሎ የሚተኛ በመሆኑ መኝታው በሚገባ የተደላደለ (የማይጎረብጥ) መሆን አለበት
– ጭንቅላታቸውን አይሸፍኑ (ከባድ ብርድ ልብስ አይጫኑ)
– ደማቅ ብርሃን ሰጪ አምፖሎች በመኝታ አካባቢው እንዲኖር አያድርጉ
– በመኝታ አካባቢው እንደ ድመትና ውሻ ያሉ የቤት እንስሳት እንዳይቀርቡ ያድርጉ፡፡

አልጋን በጋራ ስለመጠቀም

አንዳንድ ወላጆች በተለይም እንደኛ አገር ታዳጊ በሆኑ ሀገሮች የሚኖሩ ወላጆች አልጋዎቻቸውን በጋራ የሚጠቀሙበት ሁኔታ በስፋት ይታያል፡፡ በተቻለ መጠን በእናትና አባት (ወላጆች) መኝታ አቅራቢያ በቅርብ ርቀት የህፃናት መተኛ አልጋ ለብቻው ሊዘጋጅ ይመከራል፡፡ ካልተቻለና አስገዳጅ ከሆነ ህፃኑ ከወላጆች ጋር መተኛቱ አይቀርም፡፡ በዚህ ወቅት ታዲያ ወላጆች የሚከተሉትን ጥንቃቄዎች እንዲያደርጉ ይመከራሉ፡፡
– ህፃኑ የመኝታ ቦታ በቂ መሆኑን ያረጋግጡ፤ በጫፍ በኩል ከሆነ እንዳይንሸራተት ተገቢውን ጥንቃቄ ያድርጉ፡፡
– የሚለብሰው ብርድ ልብስ ከአዋቂ የተለየና ቀለል ያለ እንዲሆን ያድርጉ፡፡
– ጡት የሚጠባ ከሆነ ጡጦውን እየጠባ (በአፍ) እንደያዘ እንቅልፍ እንዲወስደው አያድርጉ፡፡ ከመተኛቱ በፊት የጡጦውን ጫፍ ከአፉ ይንቀሉ፡፡
– አልጋውን የሚጋሩት ከሆነ (እናትና አባት) ለህጻኑ ምቾትና ደህንነት ሁለቱም በጋራ ኃላፊነት ሊወስዱ ይገባል፤
– ህፃኑ የአንድ ዓመትና ከዚያ በታች ዕድሜ ላይ ከሆነ በኋላ ከሌሎች ልጆች ጋር አያስተኙት፤
– እናቶች ረዥም ፀጉር ካላቸው በህፃኑ አካል (ፊት) ላይ ሊያርፍ ይችላል፡፡ ይህ ደግሞ የህፃኑን ሰላማዊ እንቅልፍ የሚያውክ በመሆኑ እናቶች ከልጃቸው ጋር ሲተኙ ሻሽ እንዲያስሩ ይመከራሉ፤
– ህፃኑ እንዳይታፈን ተገቢውን ጥንቃቄ ያድርጉ፡፡ ምክንያቱም ከአንድ ዓመት በታች ያሉ ህፃናት በመኝታ ላይ እያሉ ድንገተኛ ለሆነ ሞት የሚጋለጡበት አጋጣሚ ሊከሰት ይችላል፡፡ በእንግሊዝ አገር በተካሄደ አንድ ጥናት አልጋን በመጋራት የሚጠቀሙ ወላጆች (ከወላጆቻቸው ጋር በአንድ አልጋ ላይ የሚተኙ ህፃናት) ለድንገተኛና ላልተጠበቀ የመታፈን ህልፈተ ህይወት ይገጥማቸዋል፡፡ በዚህም እንደ ጥናቱ ከሆነ በአንድ ዓመት ውስጥ 300 ጨቅላ ህፃናት በመኝታ ላይ እያሉ በመታፈን ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

በተሌም ከአተነፋፈስና ከልብ ጋር የተያያዘ የጤና ችግር ያለባቸው ጨቅላ ህፃናት ይህ ችግራቸው ጎልቶ ከመውጣቱ በፊት በዚህ ሁኔታ ታፍነው የሚሞቱበት ዕድል ሰፊ መሆኑን ጥናቱ አረጋግጧል፡፡ ወላች እንደ አልኮል ያሉ አስካሪ መጠጦችን የሚያዘወትሩ ከሆነ በስካር መንፈስ ሆነው ወደ አልጋ ለመኝታ ስለሚሄዱ በዚህ ወቅት ለጨቅላው ተገቢውን ጥንቃቄ ላያደርጉለት ይችላሉ፡፡ በተመሳሳይ አጫሽ ከሆኑም የሲጋራው ጢስ ለጨቅላው የምቾት እንቅልፍ ፀር ይሆናል፡፡
የአዋቂዎች አልጋ ለህፃናት ሰላማዊ እንቅልፍ ምቾት የመንሳታቸውን ጉዳይ በሚመለከት በእንግሊዝ የተካሄደው አንድ ሌላ ጥናት እንዳመለከተው ከ1,500 ቤተሰቦች 88 በመቶ የሚሆኑት ለልጆቻቸው ሰላማዊ እንቅልፍ እጦት ዋነኛ ምክንያት የሆነው ህፃናትን ከአዋቂዎች ጋር በማስተኛታቸው የሚያጋጥም ሆኖ ተገኝቷል፡፡

በእንግሊዝ የሚኖሩ 50 በመቶ የሚሆኑት እናቶች ለህፃናት ልጆቻቸው የተለየ አልጋ ለማዘጋጀት ያልቻሉ በመሆናቸው ችግሩ ተባብሶ እንደሚታይም ይኸው ጥናት አረጋግጧል፡፡ ብዙዎቹ እናቶች ልጆቻቸው ስድስት ወር ከሞላው በኋላ ከእነርሱ ጋር (ከአዋቂዎች ጋር) አንድ ላይ እንዲተኛ ያደርጋሉ ያለው ጥናቱ ይህ ሁኔታ ታዲያ ለህፃናቱ ድንገተኛ የመኝታ ላይ ሞት (በመታፈን) መንስኤ መሆኑን አመላክቷል፡፡

ለህፃናት ጤናማ እንቅልፍ እጦት ዋነኛ መንስኤ የሆነው ምቹና ሰላማዊ እንዲሁም ለደህንነታቸው አመቺ የሆነ የመኝታ አካባቢ ያለመኖር ጉዳይ ነው፡፡ በመሆኑም ወላጆች በከፍተኛ ጥንቃቄና ትኩረት ችግሩን ማስወገድ እንዲችሉ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች በሰፊው ተካሂደዋል፡፡ በእንግሊዝ ሀገር የተካሄዱት እነዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ወላጆች ለልጆቻቸው በተለይም ለጨቅላ ህፃናት ልጆቻቸው ምቹ የመንታ አካባቢ እንዲፈጥሩላቸው በማድረግ ላይ ያተኮሩ ነበሩ፡፡ በአሁኑ ወቅትም ጤናማ አስተዳደግ ለልጆች የተሰኘ ፕሮጀክት በመሰል ጉዳዮች ላይ በድረገፅ መረጃ ለወላጆች የምክር አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡

በአገራችን የሚገኙ ወላድ (እናቶች) ሌሊት ልጆቻቸው (ህፃናት) ከሰላማዊ እንቅልፋቸው ሲነቁ የእነርሱንም የሌላውንም ቤተሰብ አባላት እንቅልፍ ሲነሱ ይስተዋላል፡፡ ይህ ችግር ከየት እንደሚመነጭ ቆም ብሎ ማሰብና መፍትሄ ማበጀት ከወላጆች ይጠበቃል፡፡ የየኛ ፕሬስ የህይወት ስንክሳር አምድም ለዚህ የሚረዱ ጠቃሚ ሃሳቦችን ከጠያቂያችን አቤነዘር የሻው ጉዳይ ጋር በማያያዝ ያቀረበው ችግሩ በስፋት የሚስተዋልባቸው ቤተሰቦች (ወላጆች) ቁጥር ቀላል አለመሆኑን በመገንዘብ ጭምር ነው፡፡
ሰላም፡፡

የመንግስት ሚድያዎች ቀላል ባሉት በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ በደረሰው ቃጠሎ አንድ ተማሪ ተቃጥሎ መሞቱ ተገለጸ (የቃጠሎ ፎቶዎች ይዘናል)

$
0
0

mekele university 6
(ዘ-ሐበሻ) ዛሬ ኖቬምበር 4 ቀን 2014 ዓ.ም በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ በደረሰ ቃጠሎ አንድ ሰው ተቃጥሎ መሞቱን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታወቁ:: ዛሬ በዩኒቨርሲቲው የደረሰውን ቃጠሎ የሕወሓት አመራሮች የሚቆጣጠሩት ራድዮ ፋና “በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ አዲ-ሀቂ ካምፓስ የሚገኝ አንድ የወንድ ተማሪዎች መኖሪያ (ዶርም) ህንፃ ላይ ቀለል ያለ የእሳት ቃጠሎ ደረሰ” ሲል መዘገቡና ቃጠሎውን ማሳነሱ ብዙዎችን እንዳስቆጣም ታወቀ::
mekele university

mekele university 1
የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከመቀሌ በፎቶ ግራፍ አስደግፈው እንደዘገቡት ቃጠሎው በመንግስት ሚድያዎች እንደተዘገበው ቀለል ያለ ሳይሆን የሰው ሕይወት የጠፋበት በመሆኑ ሚዲያዎቹ በተለይ “ቀለል” ያለ ሲሉ ቃጠሎውን መግለጻቸው ከቃጠሎው በስተጀርባ የሆነ ነገር እንዳለ ያሳያል ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ::

የዘ-ሐበሻ የመቀሌ ተባባሪ ካነጋገራቸው ተማሪዎች መካከል እንደ ራድዮ ፋና ያሉ የሕወሓት ሚዲያዎች የ እሳት ቃጠሎ ትንሽ እንደሌለ ሁሉ ቃጠሎውን “ቀላል” ሲሉ መዘገባቸው አስገራሚ እንደሆነና ተቃጥሎ ከሞተው ተማሪ በስተጀርባ ምን እንዳለ ማጣራት እንደሚያስፈልግ ጠቁሟል::
mekele university 2

የመቀሌ ከተማ የፖሊስ ፅህፈትቤት ተወካይ ኮማንደር ጌታቸው ገብረህይወት በቃጠሎው ምክንያት በሰው ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱን ነው ቢያስረዱም በቃጠሎው አንድ ተማሪ ሰውነቱ ተቃጥሎ መሞቱን የዓይን እማኞች ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል::

የቃጠሎውን ፎቶዎች ይመልከቱ:-


አበበ ተካ ልጆቹን እንዲያይ በአሜሪካ ፍርድ ቤት ከተፈረደለት በኋላ ያደረገው ልብ የሚነካ ንግግር (Video)

$
0
0

ከ30 በላይ አርቲስቶች በዋሽንግተን ዲሲ ፍርድ ቤት ዛሬ የቀረበውን አርቲስት አበበ ተካን አጅበው ተገኝተው ነበር:: በዚህ የፍርድ ቤት ውሎ አበበ ተካ በተከሰሰበት ክስ ልጆቹን እንዲያይ ተፈርዶለታል:: ከዚያ በኋላ የሰጠውን ልብ የሚነካ ንግግር በምስል ይመልከቱ:-

አበበ ተካ ልጆቹን እንዲያይ በአሜሪካ ፍርድ ቤት ከተፈረደለት በኋላ ያደረገው ልብ የሚነካ ንግግር (Video)

የጥቅምት ፳፻፯ ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የመጀመሪያ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ጋዜጣዊ መግለጫ

የኢትዮጵያና የግብፅ የጋራ ሚኒስትሮች ጉባዔ የተለያዩ ስምምነቶችን በማፅደቅ ተጠናቀቀ

$
0
0
An Egyptian government minister who visited Addis Ababa earlier this week has urged Ethiopia to halt construction of a multi-billion dollar hydroelectric dam project on the Nile's upper reaches – but the request was denied.

An Egyptian government minister who visited Addis Ababa earlier this week has urged Ethiopia to halt construction of a multi-billion dollar hydroelectric dam project on the Nile’s upper reaches – but the request was denied.

ከባለፈው ቅዳሜ አንስቶ እስከ ሰኞ ድረስ የተካሄደው የኢትዮጵያና የግብፅ የጋራ ሚኒስትሮች ጉባዔ የተለያዩ ስምምነቶችን በማፅደቅና በመፈራረም ተጠናቀቀ፡፡

በግብፁ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተመራው የልዑክ ቡድን በስብስቡ ውስጥ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር፣ የትምህርት ሚኒስትርና የጤና ጥበቃ ሚኒስትር የተካተቱበት ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ አቻዎቻቸው ጋር የመግባቢያ ሰነድና ስምምነቶችን ተፈራርመዋል፡፡

በዚህም መሠረት በጤና፣ በሴቶች፣ በትምህርት፣ በንግድና በዲፕሎማሲያዊ ልምምዶች ላይ ስምምነት የተፈረመ ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ ተፈርመው ተፈጻሚ ያልሆኑ ስምምነቶችንም ለማስፈጸም በጋራ እንደሚሠሩ የሁለቱም አገሮች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ገልጸዋል፡፡

በአዲስ አበባ የተካሄደው የሁለቱ አገሮች የጋራ የሚኒስትሮች ስምምነት ላይ አገሮቹ በጋራ የሚሠሩባቸው በርካታ የንግድና የኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸው አጽንኦት ተሰጥቶበት ውይይት የተካሄደበት ሲሆን፣ ቀጣዩ ስብሰባ ከሁለት ዓመት በኋላ በካይሮ እንደሚካሄድም ተገልጿል፡፡

ከቅርብ ወራት በፊት በኢኳቶሪያል ጊኒ ርዕሰ መዲና ማላቦና በኒውዮርክ በተደረጉ ስብሰባዎች አማካይነት ሁለቱ አገሮች ውይይቶችና ስብሰባዎች ማድረጋቸው አስፈላጊ እንደሆነ መስማማታቸው ይታወሳል፡፡ በቀጣይም በተለያዩ ዘርፎች በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስብሰባ እንደሆነ ከስብሰባው በኋላ በወጣው መግለጫ ላይ ተገልጿል፡፡

ለዚሁ ስብሰባ ወደ አዲስ አበባ የመጡት የግብፁ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከኢትዮጵያ አቻቸው ጋር የተወያዩ ሲሆን፣ ‹‹ለዘመናት የቆየው የሁለቱ አገሮች የንግድ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሁለቱም አገሮች ነጋዴዎችን ማበረታታት ይገባናል፤›› ብለዋል፡፡

ምንም እንኳን የሁለቱ አገሮች የንግድ ግንኙነት መልካም ነው ቢባልም፣ ሁለቱ አገሮች ካላቸው የጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ቅርፅ የተነሳ ከዚህም በላይ መሥራት እንደሚቻል ገልጸዋል፡፡

ሁለቱም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባው በቀና መንፈስና በወዳጃዊ መልኩ መካሄዱን የገለጹ ሲሆን፣ አገሮቹ በቀጣይ የሚያደርጓቸውን ዘርፈ ብዙ ውይይቶችና ስብሰባዎች በቀና መንፈስ እንዲካሄዱ መንገድ የጠረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡

ከዚህ ስብሰባ ጎን ለጎን በሁለቱ አገሮች ባለሥልጣናት መካከል ውይይቶች የተካዱ ሲሆን፣ በጋራ የወጣው መግለጫ እንደሚያመለክተው ስብሰባው ከሁለቱ አገሮች የንግድ ግንኙነት በተጨማሪ በደቡብ ሱዳንና በቡርኪና ፋሶ ስላለው ሁኔታ እንዲሁም ስለፍልስጤም ጉዳይና ኢቦላን በተመለከቱ መወያየታቸውን ጠቁመዋል፡፡

ይህ አሁን በአዲስ አበባ የተካሄደው የጋራ የሚኒስትሮች ጉባዔ አምስተኛው ሲሆን፣ ስድስተኛ ስብሰባ ደግሞ እ.ኤ.አ. በ2016 በካይሮ እንዲሆን በመወሰን ተጠናቋል፡፡

Ethiopian Reporter

የሰማያዊ ፓርቲ የጎንደር አስተባባሪ ታሰረ

$
0
0

• ‹‹ጎንደር ውስጥ ያለውን የህዝብ ጥያቄ ለማፈን የተደረገ ነው፡፡›› አቶ ዮናታን ተስፋዬ

• ‹‹የፀረ ሽብር ህጉ የገዥው ፓርቲን ስልጣን ለመጠበቅ እየዋለ ነው፡፡›› አቶ ይድነቃቸው ከበደ

የሰማያዊ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል እና የሰሜን ጎንደር የዞን ሰብሰቢ አቶ አግባው ሰጠኝ ጎንደር ከተማ ውስጥ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በገዥው ፓርቲ ደህንነቶች መታሰሩን የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ይድነቃቸው ከበደ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
agebaw setegn
ፖሊስና የደህንነት ኃይሎች አቶ አግባው ሰጠኝን ወደ መኖሪያ ቤታቸው በመውሰድ ከ1 ሰዓት ተኩል በላይ ፍተሻ እና ብርበራ በማካሄድ ስፍራው ወደልታወቅ ቦታ እንደወሰዷቸው ጎንደር ውስጥ የሚገኙ የፓርቲ አመራርና አባላት ገልጸዋል፡፡

አቶ አግባው ከተያዘ በኋላ ጎንደር ከተማ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት እንዲሁም ዘመዶቹ ፖሊስ ጣቢያዎችን እየዞሩ ቢያጠያቁም ‹‹ነገ ጠዋት ጠይቁ!›› ከሚል ትዕዛዝ ውጭ የታሰረበትን ማወቅ እንዳልቻሉ ገልጸዋል፡፡

አቶ አግባው ሰጠኝ ከመታሰሩ በፊት የማያውቃቸው ሰዎች ለእሱ ተቆርቋሪ መምሰል ‹‹አርፈህ ስራህ ስራ፣ ከሰማያዊ ጋር የምታደርገውን እንቅስቃሴ አቁም፣ አዲስ አበባ ያሉት የፓርቲው አመራሮች ግንኙነታቸው ከሌላ ሰው ጋር ነው፡፡ ስለማታውቅ ነው፡፡›› ይሉት እንደነበር እንዲሁም ከመታሰሩ በሁለት ቀናት በፊት ከደህንነት የተላኩ ነኝ የሚል ግለሰብ ‹‹ከዚህ የማትወጣ ከሆነ በህይወት ላይ እርምጃ እንወስዳለን፣ መጀመሪያም መክረንሃል›› ብለው ይዝቱበት እንደነበር የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ኃላፊ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

ፖሊሶች የያዙት የፍርድ ቤት ማዘዣ ‹‹በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ በመሆናቸው አስፈላጊውን ፍተሻ ማካሄድ እንዲችሉ›› እንደሚል መረጃው የደረሳቸው የህግ ጉዳይ ኃላፊው ‹‹በመጀመሪያ የፀረ ሽብር አዋጁም ተቀባይነት የሌለውና የተለየ ሀሳብ ያላቸውን ሰዎች ለማሰቃየትና ገዥውን ፓርቲ ለመጠበቅ የወጣ ህግ ነው፡፡ አሁንም የምናየው በሰላማዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱ አባላት በመጠናከራቸው ለመገደብ እየተጠቀመበት ነው፡፡›› ሲል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡

በተመሳሳይ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት አቶ ዮናታን ተስፋዬ ‹‹ጎንደር አካባቢ በማህበራዊና ሌሎች ችግሮች ምክንያት በገዥው ፓርቲ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ አለ፡፡ አቶ አግባውን ጨምሮ ሌሎችም አመራሮችና አባላት ህዝቡን ስለሚያስተባብሩ ነው የታሰሩት፡፡ ጎንደር ውስጥ ያለውን የህዝብ ጥያቄ ለማፈን የተደረገ ነው፡፡ ከአሁን ቀደም አርባ ምንጭ ላይ ህዝቡ ተቀባይነት ያላቸውና ጠንካራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ አመራሮችና አባላት ላይ ተመሳሳይ እስር ተፈጽሞባቸዋል፡፡ ሌሎች አባላትና አመራሮችም አሁንም ድረስ እያዋከቧቸው ነው፡፡›› ብሏል፡፡

ኃላፊው አክሎም ‹‹በተለይ በአሁኑ ወቅት ፓርቲዎች በጋራ እየሰሩ በመሆኑ ስጋት ውስጥ የወደቀው ገዥው ፓርቲ እንቅፋት ለመፍጠር ነው እስራቱን የሚፈጽመው፡፡›› ሲል ገዥው ፓርቲ ጠንካራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉትን የፓርቲ አመራሮችና አባላት በማሰር ፓርቲውን ለማዳከም የሚያደርገው የተለመደ ስልት መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ በተመሳሳይ ሰሞኑን በመኢአድ፣ አንድነትና አረና አመራሮችና አባላት ላይም ተመሳሳይ እስር እንደተፈጸመ ተዘግቧል፡፡

በአንድ አካባቢ ኢትዮጵያዊያን ላይ  የሚካሄድ ጥቃት በሁሉም ኢትዮጵያዊ ላይ የሚካሄድ ጥቃት ነው!

$
0
0

ጥቅምት 25፣2007 (ኖቨምበር 4፣2014)

ህወሓት/ኢህአዴግ በተለያዩ ኢትዮጵያውያን ላይ ያነጣጠረ የግፍ ተግባር ማካሄድና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲውን ተግባራዊ ማድረጉን በሰፊው ቀጥሏል::  በዚህ አኳያበሶማሌ፣ በአማራው፣ በኦሮሞ፣ በሲዳማ፣ በአፋር፣….ወዘተ ተወላጆች ላይ የሚያካሂደው እልቂት በቂ መረጃ ነው::

shengoየዚህ ቀጣይ ረገጣ ተከታታይ ዒላማ የሆነው አንዱ የአማራው፡ተወላጅ ነው:: ህወሓት/ኢህአዴግ ከመነሻው የአማራ፡ተወላጁን  በጠላትነት ፈርጆ በተለያየ ደረጃየጥቃት ዒላማ አድርጎታል። በዚህም መሠረት በራሱ ትዕዛዝም ሆነ በተለጣፊ ድርጅቶቹ አማካኝነት እጅግ ዘግናኝ ግፍ የተሞላበት ወንጀል ፈጽሟል። ለዘመናት  ከኖረበት ቦታ “ወደ መጣህበት ሂድ” ተብሎ ንብረቱ ተነጥቆ ባዶ እጁን በግዳጅ እንዲባረር ተደርጓል። ይህ አልበቃ ብሎ ህፃናት ልጆች ሳይቀሩ አሰቃቂ በሆነ ግፍ እንዲታረዱ ዜጎች ወደ ገደል እንዲወረወሩና፣ ቤታቸው ውስጥ እንዳሉ እንዲቃጠሉ ተደርጓል። በአርባ ጉጉ፣ በወተር ፣በአርሲ .ወዘተ የተካሄደው ይህንኑ ነው የሚያሳየው።

ለዚህ ጨካኝና ህገወጥ ተግባርም የህወሓት/ኢህአዴግ ባለሥልጣኖች በቀጥታም በተዛዋሪም ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። በጊዜው ጠቅላይ ሚኒስተር የነበረው ታምራት ላይኔ በአማራው ተወላጅ ላይ የኦጋዴን ህዝብ እርምጃ እንዲወስድ ያካሄደው ግልጽ የሆነ መገፋፋት፣ በአርሲ በተካሄደ እልቂት እነ ኩማ ደመቅሳ ዋና ተዋናን እንደነበሩ፣ መለሰ ዜናዊ ከጉራፈርዳ የተባረሩትንና ለአቤቱታ የመጡን ዜጎች እንኳን አባረሯችሁ የሚል አንድምታ  የሚሰጥ መግለጫ በይፋ መስጠቱ ጥቂቶቹ ማስረጃዎች ናቸው።

ይህ ህወሓት/ኢህአዴግ ሆን ብሎ የሚፈጽመውና የሚያበረታታው ህዝብን እርስ በርስ የማጫረስ ተግባር እጅግ እየሰፋ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከር በአደገኛፍጥነትመም በመቀጠል ላይ ነው።

ትላንት ከትላንት በስቲያ በተለያዩ ቦታዎች እንደተደረገው ሁሉ፣ ባለፉት ጥቂት ሳምንታትም ባለማቋረጥ በጋምቤላ አካባቢ በተመሳሳይ ሁኔታ በዋናነት በዚሁ በአማራ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ የድብደባ፣ የግድያና የማፈናቀል እርምጃ በሰፊው ተካሂዶ በመዠንገር አካባቢ ብቻ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሲሞቱ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ቆስለዋል፣ በሽዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ተፈናቅለዋል።

ይህ ሁሉ ሲሆን፣ የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ግዴታ ያለበት መንግሥት መንበር ላይ የተቀመጠው ህወሓት/ኢህአዴግ ሁኔታው እንዳይከሰት ቀድሞ ለመከላከልም ሆነ በጊዜ ለማስቆም የወሰደው ምንም እርምጃ የለም። ችግሩ ከተፈጠረ በኋላም ቢሆን የተጎዱትን ለመንከባከብ፣ ህክምና የሚሹትን ለመርዳት፣ መልሶ ለማቋቋምና ወንጀለኞቹን ለህግ ለማቅረብ የሚያደርገው ይህ ነው የሚባል ሙከራ አይታይም።  ይሀ ሁሉ  የሚያመለክተው ያለው ስርዓት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የዚህ ወንጀል አካል እንደሆነ ነው።

ሸንጎው የኢትዮጵያን ህዝብ አንዱን ከአንዱ በማጋጨት ሥልጣኑን ለማራዘም ህወሓት/ኢህአዴግ የሚያካሂደውን ቀጣይ ሀላፊነት የጎደለው ኢ-ሰብአዊ ግፍ አጥብቆ ያወግዛል። በአማራውም ሆነ በሌሎች ኢትዮጵያውያን ላይ በተከታታይ እየተካሄደ ያለውን የማፈናቀል፣የግድያ፣ የጅምላ እሰራትና  ሌሎች  ወንጀሎች ባስቸኳይ እንዲቆም ያሳስባል። እስካሁን የተፈጸመው ግፍ ሁሉ ብቃት ባለው እና  ከሥርዓቱ ባለሟሎች ነፃ በሆነ አካል እንዲጣራ፤ ወንጀለኞቹም ለፍርድ እንዲቀርቡ ያስገነዝባል።

በኦጋዴን፣ በኦሮሚያ፣ በሲዳማ፣ በአፋር፣ በወልቃይት እንዲሁም በሌሎች የሀገራችን ቦታዎች ውስጥ ይህ  ሥርዓት የሚያካሂደውን ማለቂያ የሌለው ግፍ ሸንጎ አጥብቆ ያወግዛል።

ሰዎችን በትውልዳቸው የተነሳ በጅምላ የጥቃት ሰላባ ማድረግ በዓለምአቀፍ ህግም አስጠያቂ እንደሆነ የዚህ ጥፋት ፈጻሚም አስፈጻሚም የሆኑ ሁሉ እንዲገነዘቡት በድጋሚ ለማሳሰብ እንወዳለን።

የዚህን  የግፍ ሥርዓት መጨረሻ ለማፋጠን ሁሉም ኢትዮጵያዊ አንድነቱን አጠናክሮ እንዲነሳ እናሳስባለን፡  በአንድ አካባቢ ኢትዮጳያዊያን ላይ  የሚካሄድ ጥቃት በሁሉም ኢትዮጵያዊ ላይ የሚካሄድ ጥቃት ነው!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

 

ስምንት ዋና ነጥቦች ከእስራኤላውያን (ዮፍታሔ)

$
0
0

እስራኤላውያን (አይሁድ) በአንድ ወቅት ዛሬ እኛ እንዳጋጠመን የመሰለ ችግር አጋጥሟቸው መፍትሔ ፍለጋ ላይ ነበሩ። ከእኛ ችግር የነርሱ ችግር የከፋም ይመስል ነበር። ሆኖም ያን ችግር ሊፈቱት በቅተዋል። ችግሩን እንዴት ፈቱት? ምናልባት ቢጠቅም 8 ዋና ዋና ነጥቦችን ቀጥለን እንመለከታለን።

Jewish+Ethiopians+Reunited+Families+Israel+o1h5oGhsf2Vlእስራኤላውያን ከ 3000 ዓመት በፊት በግብፅ ወይም ከ2500 ዓመት በፊት በባቢሎን የደረሰባቸው በታሪክ ይታወቃል። ከዚያም ወዲህ ከ2000 ዓመት በፊት በግሪክ ሶርያውያን የደረሰባቸው ታሪክ አለ። በእነዚህ ላይ ተንታኔ ማቅረብ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ አይደለም። ከዚያ ወዲህ በሆነው ላይ (እርሱም በጣም ሰፊ ስለሆነ) በወፍ በረር በማተኮር ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ትምህርትና ላለንበት ችግር የመፍትሔ ሐሳብ በሚሆኑት ላይ ብቻ ያጠነጥናል።

ከዚህም በተጨማሪ ይህ ጽሑፍ ከእስራኤላውያን የምንማራቸውን ጠንካራ ነጥቦች እንደምሳሌ ሲያቀርብ ዛሬ እስራኤል በሌሎች ላይ (ቤተ እስራኤላውያንን ጨምሮ) የምታራምደውን ፖሊሲ በጠቅላላ እንደመደገፍ እንዳይታይ ማሳሰብ ያስፈልጋል።

ነገሩ እንዲህ ነው። ቅድመ ልደተ ክርስቶስ 63 (እ. ኤ. አ) ማለትም ከ 2,077 ዓመት በፊት ሮማውያን እየሩሳሌምን በመያዝ ይሁዳን (በጊዜው የእስራኤላውያን መኖሪያ) ተቆጣጥረው እያስገበሩ ሲያስተዳድሩ ቆዩ። ከክርስቶስ ልደት በኋላ እ.ኤ.አ በ 66 ዓ.ም አካባቢ እስራኤላውያን ግፍ ሲበዛባቸው በሮማውያን ላይ አመጹ። ሆኖም ሮማውያን አመጹን በመምታት፣ የእየሩሳሌምን ቤተመቅደስ በማቃጠልና ለጥቂት ዓመታት በኃይል የተቋቋሙዋቸውን አይሁድ በመፍጀታቸው እ.ኤ.አ በ 70 ዓ.ም አብዛኛው አይሁድ አገራቸውን ለቀው ወደውጪ ተሰደዱ። ያልተሰደዱት ደግሞ ከይሁዳና ከእየሩሳሌም ተገፍተው ወጥተው በድንበር አካባቢዎች ይኖሩ ጀመር።

ዛሬ ኢትዮጵያውያን በመላው ዓለም እንደተሰራጨነው አይሁድ የተሰደዱት በጊዜው ወደነበረው ዓለም ይልቁንም ወደአውሮፓ (ጀርመን፣ ፓላንድ፣ ሀንጋሪ፣ ፈረንሳይ፣ ኦስትሪያ፣ ስፔን፣ ራሽያ …)፣ እስያ (ኢራን፣ ኢራቅ፣ የመን) እና ሰሜን አፍሪካ ነበር።

በተሰደዱበት በተለይም በአውሮፓ አይሁድ በመጀመሪያ በባርነት ያገለግሉ እንደነበረ የሚያሳዩ ጥናቶች ይገኛሉ። በሳውዲ አረቢያ እና በሌሎችም የአረብ አገራት ዛሬ በኢትዮጵያውያን እንደሚፈጸምባቸው ዓይነት መሆኑ ነው። እየቆዩ ሲሄዱ ሁኔታዎች የተሻሻሉ መሰሉ። በየሄዱበት ሁሉ አይሁድ ከኗሪው ሕዝብ ጋር ተቀላቀሉ፣ ተጋቡ፣ ተዋለዱ፣ ጥቂት የማይባሉ ሃይማኖታቸውን ቀየሩ፣ ልጆች፣ የልጅ ልጆች ወለዱ። በመጀመሪያ የተሰደዱት በጠቅላላ አልፈው የተወለደበትን አገር አገሬ የሚል እስራኤልን የማያውቅ ትውልድ መጣ። ብዙ ትውልድ አልፎ ብዙ ተተካ።

በዚህ መካከል ግን ወደኋላ ዘራቸው እየተቆጠረና አይሁድ (Jews) ተብለው እየተለዩ በሰበብ አስባብ ጥቃት ይደርስባቸው ጀመር። ይህ ጥቃት በአገራቸው የቀሩትንም አልቀረላቸውም። እ.ኤ.አ በ 1099 “የመስቀል ጦረኞች” እየሩሳሌምን ወረው በሺህ የሚቆጠሩ አይሁዳውያንንና ሙስሊም ፍልስጤማውያንን ገደሉ። እ.ኤ.አ በ1492 የአይሁድ ዝርያ ያላቸው በጠቅላላ ከእስፓኝ ተባረሩ። እ.ኤ.አ በ1791 በሩሲያ የሚኖሩት ከቤት ንብረታቸው ተነቅለው ለብቻቸው ተለይተው እንዲኖሩ ግዞት ተበየነባቸው። ከአንደኛው አገር ጥቃት ሸሽተው የተሻለ ወደመሰላቸው ሌላ አገር ሲሰደዱና ቁጥራቸው ሲበራከት በዚያ በሄዱበት ደግሞ አዲስ ጥቃት ይከፈትባቸው ነበር። በዚህ ዓይነት በፈረንሳይ፣ በጣሊያንና በሌሎችም የአውሮፓ አገራት ጸረ-አይሁድ አዝማሚያዎች ተስፋፉ።

መገፋቱ እየጨመረ ሲመጣ በየከተማው የሚገኙት የአይሁድ ዝርያ ያላቸው (አለን ብለው የሚያምኑ) ግለሰቦች መገናኘትና መሰባሰብ ጀመሩ። የአምልኮ ስፍራዎች (Synagogues) ከሀይማኖትም በተጨማሪ እንደመገናኛና መሰባሰቢያ ማዕከላት ያገለግሉ ጀመር። ሆኖም በየከተማው የሚገኙት የአይሁድ ዝርያ ያላቸው ግለሰቦችና ማኅበራት ጥቃትን አብሮ ለመካፈል ካልሆነ በቀር ጥቃቱን የሚመክቱበት አቅም ከቶም አልነበራቸውም።

በየአገሩ ያሉት አይሁድ የማይተዋወቁና፣ የተለያየ ድብልቅ ዘር፣ ባሕል፣ የኑሮ ዘይቤና የተለያዩ አገራት ሰዎች መሆናቸው ትልቅ ፈተና ሆነ። ይህን አሰባስቦ ዘላቂ የሚሆን የመፍትሔ አቅጣጫ ማግኘት ደግሞ ከዚህም የከበደ ነበር።

ነገር ግን ወረድ ብለን እንደምንመለከተው እነዚህ ከሺህ ዓመታት በላይ በየአገሩ ተለያይተው ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ይህን ልዩነትና ታላቅ ፈተና አልፈው ተሰባስበው አገር መመሥረትና በዓለም 16ኛውን ታላቅ የዓለማችን ኢኮኖሚ መገንባት ችለዋል።

በየሄዱበት በተለያዩ ጨካኝ (ነገር ግን ጠንካራ) መንግሥታት ጫና ውስጥ የነበሩና እነርሱ ራሳቸው በብዙ ነገር ተለያይተው የነበሩ አይሁድ አንድ መሆንና ጠንካራ አገር መመሥረት ከቻሉ ሕወኀትን የመሰለ ጠባብና ምንም ዓይነት ሕዝባዊ መሠረት የሌለው ደካማ አገዛዝ አስወግደን ሰው ሰራሽ የሆነውን የእኛን በጎሳ መለያየት አሸንፈን በአንድነት ሁላችንም የምንመኛትን ጠንካራ አገር መገንባት ሊያስቸግረን አይገባም። እንዲያውም የኢትዮጵያን መፍትሔ ከነርሱ ፈጣንና ቀላል ሊያደርገው ይችላል። ነገር ግን በመጀመሪያ ከእስራኤላውያን ተግባራዊ የችግር አፈታት ብዙ የምንማረው ይኖረናል። ወደዚያ ወረድ ብለን እንደርስበታለን።

ችግሩ እየጸና ሲመጣ በየአገሩ ተበታትነው የነበሩት የአይሁድ ዝርያ ያላቸው ማኅበረሰቦች መገናኘት ጀመሩ። እ.ኤ.አ በ 1450 በጀርመን የመጀመሪያው ማተሚያ መኪና (Printing Press) በመሠራቱ ከአንድ ቦታ የሚወጣ ጽሑፍ በሌሎች አገራትም ለሚገኙ የአይሁድ ዝርያ ያላቸው ማኅበራት፣ የአምልኮ ስፍራዎች እና ግለሰቦች ይደርሳቸው ጀመር። ይህ ሁሉ ሆኖ አይሁድ ከተበተኑበት እ.ኤ.አ 70 ዓ.ም ጀምሮ እስከ እ.ኤ.አ 1894 ድረስ (ከ 1800 ዓመታት በላይ) የሚሄዱበት መንገድ የጠፋቸው መስለው ነው የቆዩት ማለት ይቻላል። በዚህ ሰፊ ጊዜ በተናጠል በየቦታው የተሞከሩ ነገሮች ቢኖሩም ለውጤት የበቃና ለሁሉም ተስፋ ሊሆን የሚችል አንድም ፍንጭ አልነበረም።

በ 1894 (እ.ኤ.አ) ግን አንድ አይሁዳዊ ዝርያ ያለው ሀንጋሪያዊ ጋዜጠኛና ደራሲ አንድ ሐሳብ በመጽሐፍ ጽፎ አስራጨ። ይህ ሰው ቴዎዶር ሄርዝል (Theodor Herzel) ይባላል። ያሰራጨው ሐሳብ አዲስ አይደለም። ከርሱ በፊት ሌላ ሰው ጽንሰሐሳቡን ተጠቅሞበታል። ጽዮናዊነት ይባላል። ይህ ስያሜ በኋላ በእስራኤል ተቃዋሚዎች ዘንድ የተለያየ መጥፎ ስም የተሰጠው ቢሆንም ‘ጽዮን’ ከሚለው በእየሩሳሌም ከሚገኝ ተራራ (አምባ) ስም የተወሰደ ነው። ቃሉ ቀድሞውንም አብዛኛው አይሁድ በሚያውቁት የሙሴ መጻሕፍት የሚገኝና ለመላው አይሁዳዊ ለመረዳት ቀላልና ግልጽ የሆነ ቃል ነበር።

“ነገር ግን ዳዊት አምባይቱን ጽዮንን ያዘ፥ እርስዋም የዳዊት ከተማ ናት።” ፪ኛ ሳሙኤል 5፡7

ነገር ግን ቴዎዶር ሄርዝል ዝርዝር መርኅግብርና ስትራቴጂ ነድፎ መጽሐፍ በማሳተም ይህንን ጽንሰሐሳብ   የሚታይ፣ የሚጨበጥና የሚያጓጓ ራእይ አደረገው።

የቴዎዶር ሄርዝል ሐሳብ በአጭሩ ይህን ግፍ ለማስቀረት አይሁዳውያን ወደምድራቸው ጽዮን ተመልሰው የራሳቸው አገር መመሥረት ይገባቸዋል የሚል ነው። በዓለማችን ታላቅ ለውጥ ያስከተሉ ሐሳቦችና ሥራዎች ቀላልና ግልጽ የሆኑት ለመሆናቸው ይህ አንድ ሌላ ምስክር ነው። ይህ ሐሳብ በየአገሩ ተበትኖ በበዙ መንገድ ተለያይቶ በነበረው አይሁዳዊ ዝርያ አለኝ ብሎ በሚያምነው ሕዝብ ዘንድ አንድ የጋራ ብሔራዊ መንፈስ ለመፍጠር የታሰበ መሆኑ ግልጽ ነበር። ቴዎዶር ሄርዝል በራሱ በኩል የእምነት ሰው ካለመሆኑም በላይ የጽዮንን (ፍልስጤም) ምድር ከዚያ በፊት ረግጦ አያውቅም።

ሆኖም የቴዎዶር ሄርዝል ሐሳብ ታላቅ ተቃውሞ ገጠመው። ተቃውሞው ደግሞ ከማንም ከሌላ ሳይሆን ከራሱ ወገኖች ከአይሁድ ነበር። ዋናው ምክንያት ከዚያ በፊት ይልቁንም በ 17ኛውና 18ኛው ክፍለዘመን አይሁድ በየሄዱበት ተመሳስለው እንዲኖሩ (ሀይማኖታዊነትን ትተው ዓለማዊ አኗኗርን በመቀበል) ከራሳቸው ወገኖች ግፊት ይደረግ ስለነበረና (“Jewish Enlightenment”) ያም የተሳካ ስለመሰለ አዲሱ ሐሳብ (ሌሎች ምክንያቶች እንደተጠበቁ ሆነው) እንደገና ተመልሰን ተለይተን እንድንታወቅና ለጥቃት እንድንጋለጥ ያደርገናል ከሚል ፍርኀት የመነጨ ነበር። “እግዚአብሔር ለአይሁዳውያን ባዘጋጀው ሐሳብ ላይ (እንደ)ማመጽ” የቆጠሩትም ነበሩ። ተቃውሞው ጠንካራ ከመሆኑ የተነሣ ቴዎዶር ሄርዝል በሙኒክ ሊያደርገው የነበረው የመጀመሪያው ጉባዔ በተቃውሞው ምክንያት ሊሳካ አልቻለም።

ቴዎዶር ሄርዝል ግን በቀጥታ አልቀበል ያሉት ወገኖቹ በተዘዋዋሪ እንዲቀበሉት ለማድረግ ከእንግሊዝ፣ ጀርመን፣ ፖላንድና ቱርክ ታላላቅ ሰዎች ጋር በየመድረኩ እየታየና በጥቂት ግለሰቦች ተግባራዊ ርዳታ እየተደረገለት ጥረቱን አላቋረጠም። በዚህም መሠረት እ.ኤ.አ በ1897 የመጀመሪያውን የአይሁድ ዓለም-አቀፍ ጉባኤ (Zionist Congress) በአብዛኛው በራሱ ወጪ በቤዝል (Basel) ስዊትዘርላንድ አካሂዶ በኋላ የዓለም ጽዮናዊነት ድርጅት (World Zionist Organization) በሚል የተሰየመው ድርጅት ሊመሠረት በቃ። የርሱ እቅድ እስራኤልን በቶሎ (1923 እ.ኤ.አ) ለመመሥረት የነበረ ቢሆንም የራሱ ወገኖች ተቃውሞ፣ ማመንታት፣ ሐሳቡን ለመቀበል መዘግየታቸውና እንግሊዝና ሌሎችም ሁኔታዎች የፈጠሩት መጓተት አይሁዳውያንን በአንደኛው የዓለም ጦርነትና ይልቁንም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት አያሌ የሕይወትና የንብረት ዋጋ አስከፍሏቸዋል።

ምንም እንኳን በዚህ ወቅት በፍልስጤም የሚኖሩ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ አይሁዳውያን ቢኖሩም ይህ ድርጅት በዳያስፖራው የተቋቋመ እንደመሆኑ (መስራቾቹም በአብዛኛው በጊዜው በጀርመን የነበሩት አይሁድ ስለነበሩ) ጽ/ቤቱን በበርሊን አደረገ። ይህ ድርጅት ለእስራኤላውያን በኋላ ያደረገውንና እስራኤልንም እስከመመሥረት እንደበቃ ስንመለከት ይህን የተቃወሙትን ሰዎች ሁሉ የሚያሳፍር እንደነበረ አይጠረጠርም። ይህ ወደመጀመሪያው ትምህርታዊ ነጥብ ይወስደናል።

  1. ድርጅት፣ ድርጅት፣ ድርጅት፤ ተቋማት፣ ተቋማት፣ ተቋማት።

(ክፍል 2 ይቀጥላል)

 

ኢትዮጵያ በቆራጥ ልጆቿ ሥራ ታፍራና ተከብራ ለዘለዓለም ትኖራለች!

 

አዲስ ንጉስ እንጂ ለውጥ መቼ መጣ?

$
0
0

አኩ ኢብን ከአፋር

በአፋርኛ
Cube waak suge ayro tewqeemih
Macal oggola anu amo ramna
cube wayni hagga yoo heekkal
anu luk suge ayro
luk raaqe.
cube wayni hagge yoo heemih
woh amo ramma yol
makko.

ይሄ ዘፈን በአማርኛ ሲተሮገም

«ያላሰብኳትን ፀሃይ ብትወጣልኝም
እኔ በነበርኩበት አለሁኝ፣
ቢሆንም ይሄ ግን አንገቴን እንድደፋ አላደረገኝም!» ይላል።

የአፋር ህዝብ በእርግጥ ያልጠበቀውን ፀሃይ ቢወጣለትም ችግሩ ግን የባሰ ሆኗል። የአፋር ህዝብ በመብቱ ፣ በሀገሩና በሃይማኖቱ በምንም አይነት መንገድ የማይደራደር በራሱ የሚተማመን ታላቅ ህዝብ ቢሆንም የወያኔ ስርዓት የአፋር ህዝብ ከፓለቲካ ጋር ያለውን ግንኙነት እንደ ደካማ ጎን በመጠቀም የአፋር ህዝብን በተዘዋዋሪ በቀኝ ግዛት እየገዛ ይገኛል። ለ23 አመታት የምንሰማው ወይም የምናየው ኢህአዴግ የብሄር ብሄረሰቦች መብትን አስከበሯል ሲባል ነው። ስለዚህም የአፋር ህዝብ ይህ የበሄር በህረሰቦች መብት ካገኙ ህዝቦች አንዱ ነውም ይሉናል። በነገራችን ላይ የብሄር ብሄረሰቦች መብት ማለት ባህላዊ ጭፈራ በመጨፈር የሚመዘን አይደለም።
afar
ይሁንና እኔ በግሌ የፈደራሊዝም ስርዓት ከሚፈለጉ አንዱ ነኝ። ግን አሁን ያለው የወያኔ የውሸት ፈደራሊዝም ሳይሆን በክልሌ ያለ ማንም ጣልቃ ገብነት ራስን በራስ መምራት ስችል፣ በቋንቋዬ መማር፣ ማስተማርና መስራት ስችል እንዲሁም በክልሌ ያለማንም ጣልቃ ገበነት የፖለቲካዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ፖሊሲ ማርቀቅ ስችል። በእነ ደብረፅዮን ሪሞት ኮንትሮል ሳልሆን ራሴ በመረጥኩት መሪ መተዳደር ስችል፣ መሪዎቼን መምረጥ ብቻ ሳይሆን አስተዳደሩን በመረጥኩበትን ቃል ጠብቆ ካላገኘሁ በነፃነት መቃውም እና ሃሳቤን በነፃነት መግልፅ ስችል፣ ወዘተ…. ያኔ መብቴ እንደተከበረልኝ እመሰክራለሁ። ግን «የአፋር ህዝብ ስለፖለቲካ አያውቅም» ብሎ በህወሃት ሪሞት ኮንትሮል በሚሰሩ ቀፎዎች «ልምራህ» ሲባል አልመራም ማለት መብቱ ነው።

በባለፉት 23 አመታት የአፋር ህዝብ እንደ ማንኛውም ዜጋ የኤሌክትረክ ብርሃን መግኘት አልቻለም። ይህን ጥያቄ አንድ የአፋር ህዝብ ተወካይ የሆኑት በፓርላማ አባል በ2002ዓ.ም አቶ መለስ በጠገኙበት አይናቸው ጭፍን አድርገው «የአፋር ህዝብ ዘላለም በጨላማ እንዲኖር የተፈረደበት ምክንያት ምንድነው?» ብለው ጠይቀው አቶ መለስ ዜናዊ ደግሞ ዘና ብለው «አዎ የአፋር ህዝብ የኤሌክትሪክ ችግር እንዳለበት እናውቃለን ግን ለኤሌክትሪክ ማመንጫ እየተገነቡ የሚገኙ ግድቦች ሲጠናቀቁ ይስተካከላል» ብለው ረዘም ያለ ቀጠሮ ሰጥተዋል። ቢሆንም ዛሬም ከጨለማ አልወጣንም መንግስት የሚባል ነገር በአፋር ክልል የለም። የአፋር ህዝብ ብሶቱን «አቤት» የሚልበት ሚዲያ የለውም። በዳሉል ወረዳ የሚገኙ 12 ቀበሌዎች ሙሉ በሙሉ መብራት የሚባል ነገር የላቸውም። ለወደፊት ተስፋ እንኳን የሚሆን የተጀመረ ስራም የለም!

ነዋሪዎች ለሚመለከተው አካል ሲጠይቁ አነሱ ደግሞ «መንገድ የለም» ይላሉ። በተለይ አንዳንድ በጐ አድራጊዎች የሆኑ የውጭ ድርጅቶች ለዳሉል ህዝብ የሚጠጣ ውኃ ለማውጣት ቢሞክሩም ማሽኑ የሚገባበት መንገድ አጥተው ይመለሳሉ። ታዲያ መንገድ መስራት ያለበት ማን ነው ? ለመሆኑ ለአፋር ክልላዊ መንግስት የሚሰጠው አመታዊ በቢሊዮኖች ብር የሚቆጠር ገንዘብ የት ነው የሚገባው? በተቀሩት 31 ወረዳዎችም ተመሳሳይ ሆኔታ ነው ያለው። እነዚህ በኢህአዴግ «የከፋፍለህ ግዛ» ህዝብን በጎሳና በዘር ለመከፋፈል የሚያባክኑት ገንዘብ የህዝብ አይደለም እንዴ? የሄ የአብዴፓ አመታዊ በዓል ሲከበር የሚያጠፉት በሚሊዮን ብሮች የሚቆጠረው ገንዘብ የህዝብ አይደለም እንዴ?

የተከበራችሁ የአፋር ህዝቦች ሆይ ይሄን ሁሉ መብቶቻችንን ለማስከበር መነሳት ያለብን አሁን ነው!!.


Sport: የትንንሾቹ የአትላንቲክ ደሴቶች የእግር ኳስ ወግ –የሴንት ሄሌና ደሴት ነዋሪዎች 4000 ብቻ ናቸው

$
0
0

- በደሴቶች ኦሎምፒክ ለመሳተፍ ይፈልጋሉ

የምናወቀው እግርኳስ በእጅጉ እየተለወጠ ነው፡፡ በዓለም እግርኳስ የቲኬት ዋጋ በእጅጉ እየናረ ነው፡፡ ቢሊየነር የክለብ ባለቤቶች ተጨዋቾችን ለማዘዋወር እና ለደመወዝ አስደንጋጭ የሆነ ከፍተኛ ገንዘብ እያወጡ ነው፡፡ ሆኖም በደቡብ አትላንቲክ ውቅያኖስ በሚገኙ ደሴቶች እግርኳስ የሚጠበቅበትን ስራ እየተወጣ ነው፡፡ ማህበረሰቦችን ወደ አንድነት ማምጣት፡፡
ሴንት ሄሌና በጣም የምትታወቀው ለፈረንሳይ የቀድሞ መሪ ናፖሊዮን ባናባርቴ የስደተኝነት መዳረሻ በመሆን ነው፡፡ ፈረንሳዊው 1821 ህይወቱ ያለው በዚህች ደሴት ነው፡፡ ደሴቷ ጠባብ ነች፡፡ የሴንት ሄሌና ህዝብ ቁጥር ከ4000 አይበልጥም፡፡ ይህ ቁጥር ይበልጥ መቀነሱ ደግሞ አይቀርም፡፡ ምክንያቱም ወጣቶቹ የደሴቷ ነዋሪዎች ለትምህርት እና ለስራ ወደ ብሪታኒያ እያመሩ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ብዙም አያስደንቅም፡፡ ምክንያቱም የሀገሪቱ ሠራተኞች ዓመታዊ አማካይ ደመወዝ 5500 ፓውንድ ብቻ ነው፡፡ ሆኖም በርካታ ችግሮች ቢኖሩበትም ሴንት ሄሌና የእግርኳስ ሊግ አላት፡፡ የእግርኳስ ማህበርም እንዲሁ፡፡
የሴንት ሄሌን የእግርኳስ ሊግ በሜይ ወር ይጀመራል፡፡ የክሪኬት የውድድር ዘመን የሚጀመረው የሊግ ማብቂያ ላይ ነው፡፡ ሴንት ሄሌና የምትመራው በብሪታኒያ ነው፡፡ ሊጉ እጅግ ከባድ ፉክክር ይደረግበታል፡፡ ተመልካቾችም ሊጉን በትኩረት ይከታተላሉ፡፡ የ2014 ሊግ 12 ክለቦች ይሳተፉበታል፡፡ እስካሁን ድረስም ከፍተኛ ፉክክር እየተደረገበት ነው፡፡ ሪቨርስ እና ሀርትስ የተባሉ ክለቦች ለሻምፒዮንነቱ እየተፎካከሩ ነው፡፡ ያለፈውን የውድድር ዘመን ሻምፒዮኖቹ የሴንት ሄሌና ዋየርበርድስ ጥሩ ጊዜን እያሳለፉ ባይሆንም በሊጉ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ ኮከብ ተጨዋቻቸው ጀንሰን ጆርጅ ደግሞ የከፍተኛ ጎል አግቢነቱን ደረጃ እየመራ ነው፡፡ እስካሁን 17 ጎሎችን አስቆጥሯል፡፡
sportfootballshot
ሴንት ሄሌና በኢንተርናሽናል እግርኳስ የመሳተፍ ህልም አላት፡፡ የደሴቷ እግርኳስ ማህበር ለ2011ዱ የደሴቶች ውድድር አንድ ቡድን ለመላክ አስባ ነበር፡፡ ውድድሩ የኦሎምፒክ መርህን የተከተለ ሲሆን በመላው ዓለም የሚገኙ ደሴቶች የሚሳተፉበት ነው፡፡ የ2011ዱ የደሴቶች ጨዋታዎች የተከናወነው በአይሰል ኦፋዌይት ነበር፡፡ እግርኳስ ማህበሩ 17 አባላት የያዘ ስኳድ ለመላክ እቅድ ነበረው፡፡ አምስቱ ከደሴቷ የሚመረጡ ሲሆን ሌሎች ደግሞ በዩናይትድ ኪንግደም የሚገኙ የሴንት ሄሌና ዝርያ ያላቸውን ተጨዋቾች ለማድረግ ታስቦ ነበር፡፡ ሆኖም ይህን እቅድ ማሳካት አልተቻለም፡፡ ህልሙ እውን መሆን ያልቻለው በፋይናንስ ችግሮች ምክንያት ነበር፡፡
የሴንት ሄሌና እግርኳስ ማህበር በቅር ከዓለም አቀፉ የእግርኳስ አስተዳዳሪ ፊፋ ጋር ግንኙነት ፈጥሯል፡፡ ሌላኛው በብሪታኒያ የተያዘው ጄብሪልተር የአውሮፓ እግርኳስ ማህበር የፊፋ አባል የማይሆንበት ምክንያት እንደሌለ ያሳያል፡፡
ሆኖም የትሪስተን ዳ ኩንሃ ደሴት ጉዳይ ከበድ ይላል፡፡ በእሳት ጎመራ በፍንዳታዎች የምትታወቀው ደሴት ከሴንት ሄሌና 1600 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ በትሪስተን ዳ ኩንሃ የሚገኙት ነዋሪዎች ቁጥር 300 ብቻ ነው፡፡ በአሳሹ ትሪስተኑ ዳ ኩንሃ ስም ለተሰየመችው ደሴት ነዋሪዎች እግርኳስ ዋነኛ የህይወታቸው አካል ነው፡፡ ስለ እግርኳስ አውርተው ከማይጠግቡት የደሴቷ ነዋሪዎች አንዱ ሊዮን ግላስ ነው፡፡ የደሴቷን የመጀመሪያ እና ብቸኛ የእግርኳስ ክለብ የመሰረተው ሊዮን ነው፡፡ ትሪስተን ዳ ኩንሃ ኤፍሲ ይሰኛል፡፡
‹‹የቴሌቪዥን ስርጭት በስፖርት ያለውን ፍላጎት በጨመረበት ወቅት የትሪስትን እግርኳስ ቡድን በ2002 ተቋቋመ›› ይላል ግላስ፡፡ ‹‹ለጉብኝት የሚመጡ ተጋጣሚዎችን ስናገኝ ከተቃራኒው ቡድን ጋር እንጫወታለን፡፡ በቅርብ ዓመታት ግን የመጡ ቡድኖች የሉም፡፡ ተጋጣሚዎች ስለሌለ ተጨማሪ ቡድኖችን ማቋቋም የሚችል አይመስለኝም፡፡ በዚያ ላይ ያለውን ቡድን ለመቀላቀል የሚፈልጉ ሰዎች ቁጥም ቀንሷል፡፡ ትረስትን ዳ ኩንሃ ኤፍሲ በዓለም እጅግ ሩቅ ቦታ የሚገኘው ክለብ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ምንም እንኳን ከዚህ በፊት ግጥሚያዎችን አድርገው ቢያውቁም (ከመርከብ ሰራተኞች ጋር ተጫውተው ያውቃሉ) ክለብ የሚገኝበት ቦታ ርቀት ጎድቷቸዋል፡፡ እንደ ሴንት ሄሌና ሁሉ ሊዮን ግለስም አንድ ቡድንን ወደ ደሴቶች ኦሎምፒክ ለመላክ ፈልጎ ነበር፡፡
‹‹እንደ ቡድን ወደ ደሴቶች ኦሎምፒክ ለመላክ ተወያይተንበት ነበረ፡፡ ነገር ግን ለጉዞው የሚያስፈልገውን ወጪ ለመሸፈን አቅም አልነበረንም፡፡ ገንዘብ እና ዕድል ካገኘን ከፍለን ወደ ውጭ ሀገራት መውሰድ እንፈልጋለን›› እያለ ሊዮን ያሉትን ችግሮች ያስረዳል፡፡ ዕድል ግን አልቀናቸውም፡፡ ተጋጣሚ ማጣታቸው ቡድኑን ወደ መፍረስ ደረጃ ሊያደርሰው ተቃርቧል፡፡ አሁን ባለ አምስት ተጫዋቾች ቡድን ሆኗል፡፡ ‹‹የዓለም ጫፍ ላይ የሚገኘው ቡድን›› የሚል ትልቅ ስም ያለው ቡድን ቢሆንም እየተቸገረ ነው፡፡ ተጋጣሚ አልባ ቡድን፡፡
ሆኖም በሌላ 1600 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ደሴት ሁኔታው የተለየ አይደለም፡፡ አሴንስን ደሴት 800 ነዋሪዎች ብቻ አሏት፡፡ አብዛኞቹ ነዋሪዎች ደግሞ የአሜሪካ፣ ብሪታኒያ እና ሴንት ሄሌና ዝርያ አለባቸው፡፡ ደሴቷ እንደ ትሪስተን ዳ ኪንሃ እና ሴንት ሄሌና የምትተዳደረው በብሪታኒያ ነው፡፡ በደሴቷ እግር ኳስ እጅግ ተወዳጁ ስፖርት ነው፡፡ አሴንስን የራሷ የእግርኳስ ሊግም አላት፡፡ ሆኖም በደሴቷ እግርኳስ ያለ ችግር አልቆመም፡፡ በደሴቷ ያለው ብቸኛው የእግርኳስ ሜዳ የተሰራው ከባህር ዳርቻ ጎን ነው፡፡ በጨዋታ ቀናት ኤሊዎችን ሜዳ ላይ መመልከትም የተለመደ ነው፡፡ ሜዳው ሣር የሚባል ነገር የለውም፡፡ ነገር ግን እንደ ሴቷ ጋዜጠኛ ካትሪን ሊዮን ከሆነ አዲስ ስታዲየም የመስራት እቅድ አለ፡፡
‹‹አዲስ ስታዲየም መገንባቱ አይቀርም፡፡ አሮጌው ደግሞ ለተወሰኑ ዓመታት ለመጫወት ያስችላል፡፡ ሎንግቢች የእግርኳስ ሜዳ ረጅም ታሪክ ስላለው ሰዎች ለመልቀቅ አልፈለጉም፡፡ አዲስ ስታዲየም ሲገነባ የተሻለ አገልግሎት መስጠት ይችላል፡፡ ሌሎች ስፖርቶችንም ያስተናግዳል፡፡ በትምህርት ቤቱ አቅራቢያ ስለሚሰራም ተማሪዎች በቀላሉ ሊጠቀሙበት ይችላሉ፡፡ ገና በደሴቷ አብዛኛዎቹ ቋሚ ነዋሪዎች አይደሉም፡፡ የሚኖሩትም የሥራ ፈቃድ አውጥተው ነው፡፡ በመሆኑም በደሴቶች ኦሎምፒክ የሚሳተፍ ቡድን ማዘጋጀት ይከብዳል፡፡ ሊጉ ግን ተጠናክሮ ቀጥሏል››
የአሴንስን እግር ኳስ ሊግ ስድስት ቡድኖች ይሳተፉበታል፡፡ ኢንሲትዊነርስ፣ ቱ ቦትስ ዩናይትድ እና ያለፈው የውድድር ዘመን ሻምፒዮኖቹ ቪሲ ሚላን ከተፎካካሪዎቹ መካከል ናቸው፡፡ እግርኳስ እጅግ ተወዳጁ ስለሆነ የደሴቱ ጋዜጣ The inslander የጨዋታ ዘገባዎችንም ትንታኔዎች ይዞ ይወጣል፡፡ ሴንት ሄሌና ሴንቲነል የተሰኘው ጋዜጣ ደግሞ የአሴንሴን ሊግ የአንድ ገፅ ሽፋን ይሰጣል፡፡ የደሴቷ ነዋሪዎች በቁጥር ትንሹ ቢሆንም በየሳምንቱ ቅዳሜ ወደ ሎንግቢች ሜዳ ለጨዋታ ይሄዳሉ፡፡ ሜዳው በኤሊዎች ተሞልቶ ወይም የባህር ውሃ ርሶ ቢያገኙትም ከመጫወት እና ከመመልከት ወደኋላ አይልም፡፡
አሴንስን ደሴትን ለቅቀው ወደ ደቡብ አቅጣጫ ሲጓዙ የፎክላንድ ደሴቶች ያገኛሉ፡፡ ደሴቶቹ በእንግሊዝ እና አርጀንቲና መካከል አስከፊ ጦርነት የተካሄደባቸው ናቸው፡፡ የፎክላንድ ደሴቶች በደቡብ አትላንቲክ ውቅያኖስ ከሚገኙት ሌሎች ደሴቶች የሚለያቸው የራሳቸው ሊግ የላቸውም፡፡ ባለፉት 10 ዓመታት የደሴቶቹ እግርኳስን የሚያስተዳድረው የፎክላንድ ደሴቶች እግር ኳስ እየተዳከ ነው፡፡ በደሴቶቹ እግርኳስን የሚያስተዳድረው የፎክላንድ ደሴቶች እግርኳስ ሊግ በ2011 ሊጉን አፍርቶበታል፡፡ ለመወዳደር የቀሩት አራት ቡድኖች ብቻ ስለነበሩ ነው፡፡ በፎክላንድ ከሪኬት የበለጠ ተወዳጁ ስለሆነ የእግር ኳስ ፍላጎት መዳከም አንደኛው ምክንያት ነው፡፡ ሆኖም ሊግ ባይኖራቸውም ፎክላንድ በደሴቶች ኦሎምፒክ መሳተፋቸውን ቀጥለዋል፡፡ የፊፋ አባል የሆነውን ቤርሙዳ እና ከአውሮፓ እግርኳስ ማህበር አባል ጂብራለታር፣ እንዲሁም አይሰል ኦፍ ማን፣ ጉኤርንሴይ እና ግሪንላንድ ጋርም ተጫውተዋል፡፡ በውድድሩ ያላቸው ሪከርድ አስደሳች አስደሳች ባይሆንም በ2013 በብሪታኒያ በምትተዳደረው ቤርሙዳ በተዘጋጀው የደሴቶች ኦሎምፒክ ላይ ሶስተኛ በመውጣት የነሃስ ሜዳሊያ ተፋልመዋል፡፡ ነገር ግን በፊፋ ደረጃ መጫወት ለፎክላንድ ደሴቶች የማይችል ይመስላል፡፡ የፎክላንድ ደሴቶች እግርኳስ ሊግ ሊቀመንበር ማይክል ቤትስም የሚጋሩት ይህንን ነው፡፡ ‹‹እንደ አጋጣሚ ሆኖ በደቡብ አሜሪካ ባለው ፖለቲካ ምክንያት ፊፋን መቀላቀል አማራጭ አይደለም››
የፎክላንድ ህልም ግን እስከ አሁን መና አልቀረም፡፡ ሊጉ በአዲስ መስክ ተጀምሮ የተደራጀ እግርኳስ በደሴቶቹ እንደሚኖር ይጠበቃል፡፡ የሊጉ አስተዳደር አርቴፊሻል ሜዳ ለማሰራት ከፎክላንድ መንግሥት ፈቃድ እየተጠባበቀ ነው፡፡ ምክንያቱም አሁን ያሉት ሜዳዎች ለጨዋታ ምቹ አይደሉም፡፡ አስቸጋሪ ንፋስ እና እጅግ ቀዝቃዛው የፈረንጆቹ በጋ የሣር ሜዳዎችን ለረጅም ጊዜ እንዳይቆዩ እያደረጋቸው ነው፡፡
በኤሊዎች ጥላ ከሚጫወት ሊግ፣ በቅርብ ካለ ተጋጣሚያቸው 1600 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ክለብ እና ለሶስት ዓመታት ይፋዊ የውድድር ግጥሚያን እስካላደረገ ክለብ የሚገኙት በእነዚህ የደቡብ አትላንቲክ ደሴቶች ነው፡፡

ኢሕአዴግ ለምርጫ አልተዘጋጀም!

$
0
0

ይድነቃቸው ከበደ

ይድነቃቸው ከበደ

ይድነቃቸው ከበደ
ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡

እንደ መግቢያ፡- በመዝገበ ቃላት አተረጓጎም መሠረት “ዲሞክራሲ ማላት በሕዝብ የተመረጠ መንግሥት ማለት ሲሆን የመጨረሻውም ሥልጣን በሕዝብ ቁጥጥር ስር ያለ፣በቀጥታ በራሳቸው ወይም እነርሱ በወከሉት ወገን ብቻ በሥራ የሚተረጐምና በነፃ ምርጫ ስርዓት የተመረኮዘ ነው” ይላል፡፡ በአብርሃም ሊንከን አባባል “ዲሞክራሲ ከሕዝብ የወጣ ፣በሕዝብ የተመረጠና ለሕዝብ የሚያገልግል መንግስት ነው፡፡”በማለት የሰጠው ትርጓሜ በአብዛኛው ተቀባይነት ያገኝ ሃሳብ ነው፡ሦስቱ መሠረታዊ የመንግስት ምሶሶዎች ተብለው የሚታወቁት ማለትም ሕግ አውጪ፣ሕግ አስፈጻሚ እና ሕግ ተርጓሚ በሁለት መንገድ ሥራቸውን ያከናውናሉ፡፡እነኚኽም አካሄዶች ቀጥተኛ እና የተወካይ ዲሞክራሲ ተብለው ተለይተው ይታወቃሉ ፡፡
election
ቀጥተኛ ዲሞክራሲ ዜጎች የሚመርጧቸው ምንም ዓይነት ተወካይ አይኖራቸውም፡፡ይህ ማላት ግን አስተዳዳሪ ወይም መሪ የላቸውም ማለት አይደለም፡፡በማናቸውም ጉዳዮች ውሳኔ የሚወስነው በቀጥተኛ የህዝብ ተሳትፎ ነው፡፡ለየትኛውም የህዝበ ውሳኔ ጉዳዮች ፣ዜጎች በጋራ ተሰባስበው በመመክር በአንድ ዓይነት ስምምነት፣ ውይም በድምፅ ብልጫ ውሳኔ የሚያስተላልፉበት ስርዓት ነው፡፡የዲሞክራሲ እናት በመባል የምትታውቀው አቴንስ ከ4 ሺህ እስከ 7ሺህ የሚደርሱ ሰዎች ስብሰባ በማካሄድ ነበር ቀጥተኛ የሆነ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን ተግባራዊ ታደርግ የነበረችው፡፡ይሁን እንጂ ከሕብረተሰብ ብዛት እና ከውስብስብነቱ አኳያ ለቀጥተኛ ዲሞክራሲ ተግባራዊነት የሚሰጠው ጥቅም ውስን በመሆኑ ብዙም ሳይጓዝ እንዲቀር ተደርጓል፡፡በአሁን ወቅት በዓለማችን በአብዛኛው ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የዲሞክራሲ ዓይነት የተወካዮች ዲሞክራሲ ነው፡፡እንዲህ ዓይነቱ ዲሞክራሲ ዜጎች የፖለቲካ ውሳኔዎችን የሚወስንላቸው ተወካዮቻቸውን በመምረጥ ነው፡፡ተመራጮችሁም በበኩላቸው የመረጣቸውን ሕዝብ ወክለው ውስብስብ መንግስታዊ ሥራዎችን እውቀታቸውን፣ጊዜያቸውን እና ጎልበታቸውን ሰውተው ግልጋሎት ይሰጣሉ፡፡

በአገራችን ኢትዮጵያ፡- ከቀጥተኛ ዲሞክራሲ ይልቅ የተወካዮች ዲሞክራሲ ውጤቱ አጥጋቢ ባይሆንም፣ ተግባራዊ ለማድረግ ሙከራዎች ከዚህ ቀደም ተደርጓአል፡፡በተለይ በቀዳማዊ ንጉሳችን ኃይለ ስላሴ የተወካዮች ዲሞክራሲ ወደ አገራችን በማስገባት የዲሞክራሲ በዓላችን እንዲዳብር የተደረገው ጥረት እና ውጤት በታሪክ በአውንታዊ ጎን ተፅፎ የሚኖር ነው፡፡ይሁን እንጂ የተወካዮቹ አመራረጥ እና የሥራ ሂደታቸው ሲለካ ውጤቱ ምን እንደነበር ለታሪክ አዋቂዎች ቢተዉ የተሻለ ይሆናል፡፡ከዚህ ባለፈ በደርግ የተካሄደው የብሔራዊ ሸንጎ እና የኢሕአዴግ የ4 ዙር አገር አቀፍ ምርጫ ለዜጎች ከሰጠው ፋይዳ ይልቅ የአምባገነን ሥርዓት ለማስቀጠል የሰጠው ጥቅም የበዛ ነው፡፡

ከምርጫ 1997 ዓ.ም ወዲህ፣ ገዥው መንግሰት የምርጫን መቃረብ ተከትሎ መንገዶችን ይሰራል፣ የጋራ መኖራይ ቤት ገንብቶ በዱቢ እና በረጅም ወራት ክፍያ ለተጠቃሚዎች ያስተላልፋል፣ለመንግሰት ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ያደርጋል፣በአንድ ለአምስት አደረጃጀት በመጠቀም የምረጡኝ ዘመቻ ይጀምራል፣አብዮታዊ ዲሞክራሲ ስልጠናና ጥምቀትን ያካሂዳል፣ዘላቂነት የሌላቸው ጊዚያዊ የሥራ እድሎችን በመፍጠር የሥራ አጦችን ካርድ ይነጥቃል፤ይህ ሣይሆን ሲቀር ኢ-ፍህታዊ ጥቅማ-ጥቅምን በመስጠት ደጋፊን ያበዛል፡፡ በተጨማሪም መቼም የማይፈፀሙ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በየቦታው የመሠረት ድንጋይ በመጣል ዳንኪራ ያስጨፍራል፣ከዚህም በላይ የሆነበትን ደግሞ ቃል ይገባል ፡፡እነዚህና መሰል የሆኑ ሁሉ ነገሮችን ማከናወኑ ለምርጫ ካርድ እንጂ ለዘለቂታዊ ልማት አይደልም፡፡የምርጫ ወቅት ሲቃረብ መንግስት ደፋ ቀና ደፈ ቀና የሚለበት ሥራ ሁሉ ለይስሙላ እንጂ ዘለቄታዊ ጠቀሜታ እንደሌለው ላለፉት አራት ዙር በተደረጉ ምርጫዎች ለማረጋገጥ ይቻላል ፡፡ በይበልጥ ደግሞ የፊታችን ግንቦት ወር ይካሄዳል የሚባለው ምርጭ በገዥው መንግሰት ቀጥተኛ ተፅኖ ስር በወደቀው ምርጫ ቦርድ እና ፣በመንግስት በኩል መንገስት ስል ኢሕአዴግ ወይም ወያኔ ለማለት እንደተፈለገ ግንዛቤ ይወሰድልኝ፡፡ምክንያቱ ደግሞ ገዥው ፓርቲ እና መንግስት ባልተለያዩበት ሥርዓት ውስጥ በመሆናችን ነው፡፡ስለሀኖም በእነዚህ ሁለት ሃይሎች ተፎካካሪ ወይንም አማራጭ በሆኑ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ ይህ-ቀረሽ የማይባል ጫና እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡ችግሩ ደግሞ ቀጥተኛ በሆነ መንግድ የሚፈፀም ስለመሆኑ ከዚህ በታች በመጠኑ ለማመላከት ይሞከራል፡፡

የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በፓርቲዎች፡-
በዓለም አቀፍ የተባበሩት መግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ጉባሄ ባፀደቀው መግለጫ ኢትዮጵያም በፈረመችው ስለ መሰብሰብ እና መደራጀት መብቶች በሚከተሉው መልኩ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ “ የዜጎች የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ተግባራዊ ሂደት ገደብ በማይጣልበት ሁኔታ መከበር ሲኖርበት ነገር ግን ገደብ ቢደረግ እንኳን ገደቡ የዓለም ዓቀፍ ህግና ሰብዓዊ መብቶችን መሰረት ያደረገ እና የእነዚህን መብቶች ሁለንተናዊ ጥበቃ እዉን የሚያደርግ መሆን አለበት፡፡በተለይም ዜጎች የፖለቲካ እና የአይማኖት ለማስከበር የሚያደርጓቸው ተቃውሞዎች መደገፍ አለባቸው፡፡”የሚል ነው ፡፡

ይህ እጅግ በጣም ጠንካራ የሆነ ዜጎች በፖለቲካ የመደራጀት መብታቸውን የሚያስከበር ዓለም አቀፍ ሕግ ነው፡፡አሁን በሥራ ላይ ያለው ሕገመንገስት ይህን ህግ በመቀበል አካቶ ይገኛል፡፡እርግጥ ነው ህገመንግስቱ በራሱ ማሻሻይን የሚፈልጉ በርካታ አንቀፆች አሉት፡፡በዚህ አጋጣሚ ሰማያዊ ፓርቲ ዜጎችን በጋራ አግባብቶ በዘላቂነት ሊያገለግል የሚችል እና ለሕገመንግሰት መሠረት ወይም ምሶሶ የሚሆን “የዜጎች ቃል-ኪዳን ሰነድ ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ”የተሰኘ ሠነድ በማዘጋጀት ለህዝብ ይፋ ማድረጉ የሚታወቅ ነው፡፡ለዚህም መልካም ጅማሮ ለሰማያዊ ፓርቲ አድናቆት ሊቸረው ይገባል፡፡ወደጉዳያችን ስንመለስ በዓለም አቀፍ እዲሁም በኢትዮጵያ ሕግ የፖለቲካን ዓላማ ለማስፈፀም ሕግን መሠረት ያደረገ አደረጃጀት የተፈቀደ ነው፡፡ይሁን እንጂ ይህን መሰረት ያደረገ አደረጃጀት ኖራቸው በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የተቃወሚ ፓርቲዎች፤ ሰብዓዊና ዲሞክራሳዊ መብቶች ይከበሩ፣የሕግ የበላይነት ይረጋገጥ፣ህዛባዊ መንግሰት ይመስረት በማለታቸው እና ለተግባራዊነቱ በመንቀሳቀሳቸው ብቻ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ለሞት፣ለእስራት፣ለስደት እና ለእንግልት እየተዳረጉ ይገኛሉ፡፡

ይህም በመሆኑ አብዛኛው የተቃዋሚ ፓርቲ አባላቶቺ ታስረዋል፣የመንግሰት ታጣቂ ሃይሎች በግልፅ እና በስውር በፓርቲ አባላት ወከባና እንግልት እየፈፀሙ ይገኛሉ፣ጠንካራ የሚባሉ የተቃዋሚ ሃይሎች የቀን-ተቀን ሥራቸውን የሚያከናውኑበት ቢሮ መከራየት እንዳይችሉ አከራዩች በቀበሌ ካድሬዎች ማስፈራሪያ እና ዛቻ ይደርስባቸዋል፣ከብዙ ልፋት እና እንግልት በኋላ በሚያገኙት ቢሮ የፓርቲ አባላቶች ወደ ቢሮ ሲገብ እና ሲወጡ እየጠበቁ የመንግሰት ደንነቶች ወከባ ከፍ ሲልም ትንኮስ እየፈፀሙ ይገኛሉ፣ ፓርቲዎች ዋንኛ የተቋቋሙለትን ዓላማ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችላቸውን ማናቸውም እንቅስቃሴዎች ከደጋፊዎቻቸው ጋር በመሆን በነፃነት አደባባይ ወጥተው ቅስቀሳ እንዲሁም ተቃውሞ ማድረግ የሞት ሽረት ትግል ነው፡፡በተለይ ደግሞ አዲስ ተመዝጋቢ አባላት የአባልነታው የእጩ ቀናት መቁጠር ከመጀመራቸው በፊት በመንግሰት ታጣቂ እና በካድሬዎች የሚደርስባቸው ማስፈራሪያ እና ዛቻ ልጉድ ነው፡፡ከምንም በላይ ደግሞ የአባላትን ወራዊ መዋጮ እና ድጋፍ የፓርቲዎች የፋይናስ አቅም አይነተኛ መንግድ ነው፡፡ሆኖም ግን ይህ ገንዘብ በራሱ በቂ አይደለም፡፡ይህም በመሆኑ የፓርቲ አባላት ሣይሆኑ ደግፍ መስጠት ለሚፈልግ ለማንኛውም ኢትዮጵያዊ በልብ ሙሉነት ገንዘባቸውን እንዳይለግሱ ጫና ይደረግባቸዋል፡፡የጉዳዩ አሳሳቢነት ምን ያኸል እነደሆነ ለማሳያ አነድ ምሣሌ መጥቀስ ይቻልል፤አቶ የሺዋስ አሰፋ፣አቶ አብታሙ አያሌው፣አቶ ደንኤል ሽበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ በማእከላዊ እስር ቤት በዋንኛነት የሚደረግባቸው ምርመራ “የፓርቲያችሁ የገንዘብ ምንጭ ምንድነው ? ማነው በቋሚነት ድጋፍ የሚያደርግላችሁ ?ገንዘቡ የት ነው የሚቀመጠው” የሚሉት ዘወትር የተለያየ የምርመራ ዘዴዎች በመጠቀም የሚጠየቁት ጥያቄ ነው፡፡ነገሩን ይበልጥ አስገራሚ የሚያደርገው ከላይ የተገለፁት የፓርቲ አባለት የተያዙት “በሽብር ወንጀል በመጠርጠር ነው”በማለት ገዥው መንግስት ገልፆአል ሆኖም በምርመራ ወቅት ግን የሚጠየቁት የፓርቲ ገንዘብ ወጪና ገቢ ነው፡፡ በአጠቃላይ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል በመሆን ብቻ ነጋዴው ከንግዱ፣ተማሪው ከት/ት፣ሰራተኛው ከስራው፣ገበሬው ከእርሻው፣አርብቶ አደሩ ከከብቶችሁ እየተፈናቀለ ይገኛል፡፡

ስለዚህም ተፈካካሪን የተቃወሚ ፓርቲን በእንዲህ መልኩ እያዳከመ እና አንዳንዶችን በጭራሽ ከወደቁበት እንዳይነሱ እያደረገ ይገኛል፡፡በእንዲህ መልኩ ከሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ጋር ኢሕአዴግ ተፎካካሪ በመሆን ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው እንዴት ሊባል ይቻላል ?

የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በምርጫ ቦርድ ፡-
በየደረጃው ትክክለኛ ምርጫ እንዲካሄድ ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ይቋቋማል፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 102 ላይ ይገኛል፡፡ይሁን እንጂ የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች ሹመታቸው ከመንግስት መልካም ፍቃድ የመነጨ ሲሆን አሰራራቸውም ለገዥው መንግስ በእጅጉ በጣም ያደላ ነው፡፡ስለዚህም ምርጫ ቦርድ ህገመንግስቱን መሠረት አድርጎ ነጻ እና ገለልተኛ ነው ለማለት ከበድ ድፍረትን የሚጠይቅ ነው፡፡የስከዛሬውም የምርጫ ቦርድ የሥራ አንቅስቃሴ ለገዥው መንግስት ያለው ታማኝነት እና አገልጋይነት በድብቅ ሣይሆን በአደባባይ “እዩልኝ፣ስሙልኝ” እያለ በራሱ ላይ መስክሮ የእኛን መስክርነት ከሰጠን አመታት ተቆጠሩ፡፡ከወረዳ የምርጫ አስፈፃሚ ጀምሮ እስከላይ ያለው የምርጫ ቦርድ ሃላፊ፣ በገዥው መንግሰት ቀጥተኛ ተፅእኖ ስር መሆናቸው ግልፅ እና አሻሚ ያልሆነ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ ላይ ከዘህ በላይ ማሣያዎችን ለማመላከት መሄድ ዉሃ ቅዳ ዉሃ መልስ ይሆናል ነገሩ፡፡

በመሆኑም ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በአገራችን የለም፡፡ ሃቁ ይህ ሆኖ ሣለ ከተፈካካሪ የተቃወሚ ፓርቲዎች ጋር ኢሕአዴግ ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው ማለት እንዴት ይቻላል ?
የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በነፃ በጋዜጠኛ ላይ ፡-
ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት የአመለካከት እና ሐሳብን በነፃ የመያዝና በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ የመግለፅ ነፃነት አለው፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 29 ተፅፎ ይገኛል፡፡ በእርግጥ ይህ መብት ገደብ ሊጣልበት እንደሚችል በህገ መንግስቱ ላይ ተገልፆ የተቀመጠ ሲሆን ገደብ ግን መሠረታዊ የሆነውን መረጃን የመስጠት እና የማግኘት እንዲሁም አስተሳሰብ ላይ ወይም አመለካከት ላይ ውጤት እንደማይኖረው በህገመንግስቱ ተገልፆ ይገኛል፡፡

ይሁን እንጂ አሳብን በነፃ ማሰብና ማንሸራሸር በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ እጅግ አዳጋች ነው፡፡ አሳብን ለመግለፅ ይቅርና ከገዥው መንግስት ፍላጎት እና አሳብ ውጪ ማሰብ በራሱ ለእስራት እና ለእንግልት ይዳርጋል፡፡ጋዜጠኞችን በማሰቃየት፣በማሰር እና እንዲሰደዱ በማደረግ ኢትዮጵያ በዓለማችን መጥፎ ሪከረድ አስመዝግባለች፡፡በአሁን ወቅት ከ17 የማያንሱ ጋዜጠኞች በእስር ቤት እየተሰቃዩ ይገኛሉ፡፡21 የሚሆኑ ጋዜጠኖች በስደት መከራን እየተቀበሉ ነው፡፡መንግስትን ተችቶ የፃፈና ፁሁፉ የወጣበት ጋዜጣ ወይም መፅሔት ጨምሮ ሁሉም ተጠራርጎ ቃሊቲ የሚገባበት ወይም አደገኛ ዛቻና መስጠንቀቂያ የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡በውጪ አገር የሚገኙ የተለያዩ ሚዲያዎችም ቢሆኑ፣በአገር ውስጥ ተደማጭ እና ተነባቢ እንዳይሆኑ ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ አፈና እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡

ስለዚህም ነፃ አሳብ የሚንሸራሸርባቸው ነፃ ጋዜጦችና መፅሔቶች ምን ያህል አሉ ? በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሄደው አገራዊ ምርጫ ተፈካካሪ ፓርቲዎች የምረጡኝ ዘመቻ ቅስቀሳ የሚያደርጉት በይትኛው ነፃ ጋዜጣ እና መፅሔት ነው ? ህሊናውን እና ሙያውን ብቻ መሠረት አድርጎ የሚሰራ ጋዜጠኛ ምን ያህል አለ ? እርግጥ ይህ ፁሑፍ የቀረበበት ሚዲያ ጋዜጣ በቀጣይ የሌሎች ጋዜጣ እና ጋዜጠኞች እጣ ፈንታ እንደማይደረሰው በምንም እርግጠኛ መሆን ይቻላል፡፡በምንም!!
እናም ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ጋዜጠኛ እና የእትመት ውጤት ሣይኖር መርጫ እንዴት ይታሰባል፡፡አገራችን በጋዜጠኛ ድርቅ እንድትመታ ገዥው መንግሰት ሆነ ብሎ ያደረገው መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ይህ በሆነበት ሁኔታ ኢሕአዴግ ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው ማለት በራስ ላይ እንደመተኮስ ይቆጠራል ፡፡

ከላይ በመጠኑ የዚህ ፁሑፍ አቅራቢ ለመዳሰስ የሞከራቸው እና ሌሎች ተመሳሳይ ምክንያቶችን ግምት ውስጥ በማስገባት፣ ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !

የልጅቷ እምባ –ከሳዑዲ አረቢያ መልስ – (እውነተኛ የወንጀል ታሪክ)

$
0
0

እመቤት ከአራት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሯ በመመለሷ ደስተኛ ሆናለች፡፡ በ1993 ዓ.ም መስከረም ወር አካባቢ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ስትጓዝ መንገዱ አልጋ በአልጋ ሆኖላት አልነበረም፡፡ ከ10 ክፍል በላይ ልትቀጥለው ያልቻለችውን ትምህርት ትታ አዲስ አበባ ውስጥ መቀመጥ አልታያትም፡፡ የተወለደችውና ያደገችው ጅማ ቢሆንም ወደ አዲስ አበባ ከመጣች ግን ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ እናቷ ወታደር አባቷን ተከትለው ሸገር ሲገቡ እሷ በአያቷ እጅ ነው ያደገችው፡፡ አያቷ ከልጅነቷ ስላሳደጓት እናትና አባት ጅማን ለቀው ወደ አዲስ አበባ ለመክተም ጓዛቸውን ሲጠቀለልጁ ‹‹እሷን ከእኔ ነጥላችሁ ከወሰዳችሁ እናት አለኝ ብለሽ እንዳትመጪ- እንደሞትኩ ቁጠሪኝ›› ብለው ስለተማረሩ ነው እመቤት እዚያው እንድትቀር የተወሰነው፡፡ የመጀመሪያ ልጅ ብትሆንም ወትሮም ከእናትና አባቷ ይልቅ የምታውቀው የአያቷን ጣእም ነውና ከርሳቸው ተለይታ ወላጆቿን ተከትላ አዲስ አበባ መግባትን አልወደደችም፡፡ አድጋና ነፍስ አውቃ 8ኛ ክፍልን ስትጨርስ ግን አዲስ አበባ መጥታ መማር እንዳለባት የወሰነችው ራሷ ናት፡፡ አንድም ያሳደጓት አያቷ በድንገተኛ ህመም የ7ኛ ክፍል ተማሪ ሳለች በማረፋቸው ሌላም አዲስ አበባ ገብታ ብትማር የተሻለ መሆኑን ስላሰበች እናትም ስለገፋፏት ነው ሸገር የገባችው፡፡
crime
ዛሬ 10ኛ ክፍልን ብታጠናቅቅም ከዚያ በላይ ለመግፋት የሚያስችል ነጥብ አልመጣላትም፡፡ ስለዚህ ስራ ከመፍታት ብላ በተለያዩ ካፍቴሪያዎች ውስጥ የአስተናጋጅነት ስራ ሞክራለች፡፡ ነገሩ ‹‹ከእጅ አይሻል ዶማ›› ሲሆንባት ነው ወደ ውጪ ሀገር ስለመጓዝ ማለም የጀመረችው፡፡ በወቅቱ በቀላሉ ልትጓዝበት የምትችልበት መንገድ የሃጂና ዑምራ ጉዞ ነው፡፡ አንድ ሰው በደላላ አግኝታ የእርሱ ሚስት እንደሆነች ተደርጎ በሙስሊም ስም ፓስፖርት ካወጣችና ኒካ ካሰረች በኋላ ፕሮሰሱ ብዙ አልቸገራትም፡፡ ከወላጆቿ አስቸግራና ራሷም ያጠራቀመችውን ገንዘብ ጨምራ በ6 ሺ ብር ወጪ ከሃጅና ዑምራ ተጓዦች ጋር ተቀላቅላ ዘይነባ በሚል ስም ሳዑዲ ገባች፡፡ አራት ዓመታትን ያሳለፈችው በተለያዩ ቦታዎች የቤት ሠራተኛ ሆና በማገልገል ነበር፡፡
ዛሬ አዲስ አበባ ስትመለስ የተሰማት ስሜት ልዩ ነበር፡፡ ወላጆቿን ማግኘቷና ታናናሽ እህትና ወንድሞቿን አድገው ማየቷ- ከዚህም በላይ የናፈቀችውን አገሯን ደግሞ ለመመልከት በመታደሏ ደስ ብሏታል፡፡ አመጣጧ ለእረፍት ሲሆን ከ5 ወር በኋላ በሌላ ወረቀት ወደ መጣችበት አገር ለመመለስ እቅድ ይዛለች፡፡

ጊዜዋን ከወላጆቿና ከምታውቃቸው ጓደኞቿ ጋር እያሳለፈች ነው፡፡ አዲስ አበባ ከገባች ከ15 ቀናት በኋላ ነበር ወደ ጅማ ሄዳ ዘምድ ወዳጆቿን ለመጠየቅ የተነሳችው፡፡ እናቷ አብረዋት ሊሄዱ ከተነሱ በኋላ የግል ጉዳይ ስለገጠማቸው በሌላ ቀን ሊመጡ ተነጋግረው ነው ብቻዋን የተጓዘችው፡፡ ለዘመድ አዝማድ የሚሰጡትን ስጦታዎችና የገዛቻቸውን ነገሮች ይዛ በአውቶብስ ወደ አባ ጅፋር ሀገር ጉዞ ጀመረች፡፡ ይህ ጉዞ ለእመቤት ዘመዶቿንና የናፈቋትን ጓደኞቿን የምታይበት ብቻ ሆኖ አልቀረም፡፡ በመንገዱ ላይ አጠገቧ ተቀምጦ ከነበር አንድ ሰው ጋር ለመተዋወቅ እድል ፈጥሮላታል፡፡

ጋሻው በዚያን ዕለት ወደ ጅማ የሚጓዘው ከአዲስ አበባ በስራ ምክንያት ተቀይሮ የሄደ የልብ ጓደኛ ሀገሩን እንያይ ባቀረበለት ግብዣ መሰረት ነው፡፡ ስለሆነም ጅማ ላይ ተጨማሪ ጓደኛ ልትሆነው የምትችል ልጅ ሲያገኝ ስለሀገሩም ስለራሷም አንዳንድ ነገሮችን እየጠየቃት ተግባብተው ነው መንገዱን የጨረሱት፡፡ በጉዟቸው ላይ እመቤት ለጋሻው ሁሉንም ታሪኳን ነግራዋለች፡፡ ከውጪ መምጣቷንና ቤተሰብ ለመጠየቅ የምትሄድ መሆኑን ጭምር፡፡ ለረጅም ጊዜ የሚተዋወቁ ያህል ብዙ የተጨዋወቱትና ስለራሳቸው መረጃ የተለዋወጡት የጉዞ ጓደኞች አጋጣሚውን ወደውታል፡፡ እመቤት በተለይ ረጅሙን ጉዞ የሚያቀልላት አጫዋች በማግኘቷ ተደስታለች፡፡ እሱም በልጅቷ ውበትና ሳቂታነት ተማርኳል፡፡ ጅማ ሲገቡ ደግሞ መገናኘት የሚችሉበትን ዕድል አመቻችተው ነበር የተለያዩት ስልክ ተለዋውጠዋል፡፡ እመቤትን አውቶብስ ተራ ሲጠብቋት የነበሩት ዘመዶቿ ሲቀበሏት ጋሻውን ጓደኛው መጥቶ ወስዶታል፡፡ በዚህ አጋጣሚ የተገናኙት ሁለቱ ሰዎች ከዚያን ቀን ጀምሮ አንዳቸው ለሌላኛቸው አስፈላጊ ሰዎች መሆናቸው እስኪሰማቸው ድረስ ቅርርባቸው ጠንክሮ ነበር፡፡

ጅማ መንገዱ ላይ የተጀመረው ትውውቅና በዚያች ከተማ ያሳለፏት የጥቂት ቀናት የጓደኝነት ቆይታ የተጠናከረው አዲስ አበባ ከተመለሱ በኋላ ነው፡፡ ጋሻው ለእመቤት በጣም ጥሩ ሰው ሆኖ ነው የቆየው፡፡ እመቤት በጋሻው ጥሩነት፣ አሳቢነትና መካሪነት እንዲሁም የልቧን ልታጫውተው የምትችል ሁነኛና ቁም ነገረኛ ሰው መሆን በጣም ነበር የተደሰተችው፡፡ በየዕለቱ እየተደዋወሉና በየዕለቱ እየተገናኙ ግንኙነታቸውን ከተራ ጓደኝነት ወደ ፍቅር አሳደጉት፡፡ እመቤት ጋሻውን ወዳዋለች፡፡ ለረጅም ጊዜ የምታውቀው ያህል አክብራዋለች፡፡ በተለይ ለርሷ አሳቢነቱና በማንኛውም ሁኔታ በህይወቷ ውስጥ ጠቃሚ ሰው መሆን እንደሚችል በሚሰጣት አክብሮትና ፍቅር ማረጋገጥ መቻሉ የዚህችን ወጣት ልብ በቀላሉ ለመግዛት አስችሎታል፡፡

አንዳቸው ስለሌላቸው የሚያውቁት አንዳች ነገር የሌለ እስኪመስል ድረስ የየግል መረጃዎቻቸውን ሁሉ ተለዋውጠዋል፡፡ እመቤት የምታውቀው ጋሻው ብዙ ጊዜ ትዳር ለመመስረት ሞክሮ ያልተሳካለት በሚያከብራቸውና ሁሉን ነገር በሰጣቸው ሴቶች የተከዳ ከአንዴም ሁለቴ ህልሙን በናዱበት ፍቅረኞቹ የተጎዳ መሆኑን ነው፡፡ እርሱ ጥሩ ሆኖ ሳለ ያጋጠሙት ሴቶች ታማኝና የትዳር ሰው ለመሆን ባለመቻላቸው ውስጡ እጅግ መጎዳቱን በዚህ የተነሳም ከዚህ ወዲያ ፍቅር የሚለውን ነገር ፈጽሞ እንደማይሞክረው ለራሱ ቃል ገብቶ የነበረ ሰው መሆኑን ነው የምታውቀው፡፡ በመሀል ከእርሷ ጋር ሲተዋወቅ ከዚህ ጥርጣሬ ጋር ሆኖ ስለነበር ደጋግሞ በእርግጥም ልቡን እንደማታደማውና ያለፉት ያስቀየሙትን እንደማትደግመው እየመላለሰ ጠይቋት ያረጋገጠ በመሆኑ በነገራት ታሪክ ላይ አንዳች ጥርጣሬ አላደረባትም፡፡ እሷም የምትፈልገው ታማኝና ቃሉን አክባሪ እንዲሁም ለጊዜያዊ ግንኙነት ሳይሆን ለዘላቂ ትዳር ራሱን ያዘጋጀ ሰው ስለሆነ በዚህ በኩል እንደ ተሳካለት አምናለች፡፡ አንዳቸው ለሌላቸው እግዚአብሔር የጣለላቸው ገፀ በረከት መሆናቸውን አምነዋል፡፡ በተለይ እመቤት የወደፊት የትዳር አጣማጇን ባግኘቷ ውስጧ በደስታ ሰክሯል፡፡ ጥሩ ጊዜ አሳለፉ- በፍቅር እንዲህ ልቧ በመጥፋት የመጀመሪያዋ የሆነው እመቤት ጋሻውን ወደደችው ብቻ ሳይሆን አመለከችው ማለት ይቀላል፡፡ የቅርብ ጓደኛዋ አምሳለ እንዳለችው የሁለቱ ፍቅር እመቤት ጋሻው ያላትን ሁሉ ከመፈፀምና እያንዳንዱን እንቅስቃሴዋን ከእርሱ ፍላጎትና ጥያቄ ጋር የማጣጣም ባህሪ ከማዳበር ባለፈ ለጋራ ኑሮ ጎጆ እስከመቀለስ እቅድ አድርሷቸዋል፡፡ ይህ ሁሉ ሆኖ ታዲ እመቤት ጋሻውን እንጂ አካባቢውን አታውቀውም፡፡

በአንድ የግል ድርጅት ውስጥ በአክርቴክትነት እንደሚሰራ፣ ጦር ኃይሎች አካባቢ ከእናቱ ጋር እንደሚኖርና የሚያስተምራቸው ሁለት ታናናሾች እንዳሉት፣ አባቱ መሞታቸውን፣ እናቱ ዘወትር እንዲያገባ እንደሚጨቀጭቁት እሱ ደግሞ የቤተሰቡ ነገር እንደሚያስጨንቀው ነው የነገራት፡፡ አምሳለ በዚህ ሁለት ወር ጊዜ ውስጥ እመቤት ስለ ጋሻው ያወራችው ነገር ሁሉ እውንት ስለመሆኑ ከእርሷ ውጪ ለሌላ አካል መረጃ ስለሌላት ጓደኛዋ ያለቻትን አምና ከመቀበል ውጪ አማራጭ አልነበራትም፡፡ ጋሻው አንድም ሰው ለመተዋወቅ ስለማይፈልግና ‹‹ጓደኛ ፍቅር ያደፈርሳል እንጂ አይጠቅምም›› የሚል አቋም ስለነበረው እመቤት ጓደኛዋን ልታስተዋውቀው- አምሳለም በዚህ አጋጣሚ ጋሻውን ልታየው አልቻለችም፡፡ ስለዚህ ስለርሱ የምትሰማው እመቤት በምትነግራት ወሬ ነው፡፡

በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ እመቤት ቲኬቷ የሚቃጠልበት ጊዜ ደረሰ፡፡ በ3 ወር ውስጥ ለመመለስ ይዛ የነበረውን እቅድ ለማክበር አልቻለችም፡፡ ጋሻውን ተለይታ መሄድ የማይሆን ሆነባት፡፡ ናፍቆቱን የምትችለውም አልመሰላትም፡፡ በዚህ ሳቢያ መወሰን አቅቷት መዋለል ጀመረች፡፡ በዚህ በኩል ጋሻው ተመልሳ እንዳትሄድ ይወተውታታል፡፡ በተለይ ደግሞ በፍቅር መካከል የሚፈጠር ክፍተት ለችግር እንደሚዳርግ በመንገር መለያየታቸው ክፉ ነገር ይዞ እንደሚመጣ ያስረዳታል፡፡ በሌላ በኩል ቤተሰቦቿ እዚህ መቀመጥ እንደሌለባት ይወተውቷታል፡፡ በተለይ አዲስ ባመጣችው ባህሪና ሁሌም ውጪ ውጪ በማለቷ ገንዘቧን እያባከነች መሆኑ የተሰማቸው እናቷ ቶሎ ወደመጣችበት እንድትመለስ ይጨቀጭቋት ነበር፡፡ ከዚህ ሁሉ በኋላ ያሸነፈው ሃሳብ የጋሻው ሆነ፡፡ እመቤት ወደ ውጪ ተመልሳ የመሄድ ሃሳቧን ሰረዘች፡፡ አሁን ሙሉ ምርጫዋና የወደፊት እቅዷ በጋሻው እጅ ገብቷል፡፡

አብሮነት

ሁለቱ ጥንዶች በተዋወቁ በ6ኛው ወር ነው አብረው የመኖር ሃሳብ ያመጡት፡፡ ጋሻው እመቤትን ቤት ተከራይተው መኖር እንደሚገባቸው ይወተውታት ያዘ፡፡ አራት ዓመት ሰርታ ያመጣችውን 78 ሺ ብር ህይወታቸውን ለመመስረት ሊጠቀሙበት እንደሚገባም ይጨቀጭቃት ጀምሯል፡፡ እመቤት በዚህ ፍጥነት የጠየቃትን አብሮ የመኖር ጥያቄ ለመመለስ ተቸገረች፡፡ በተለይ የጓደኛዋ ተደጋጋ ማስጠንቀቂያ ከቤተሰቦቿ ጋር የፈጠረችው ግጭት ጥቂት ወደ ራሷ እንድታስብ ቢያደርጋትም ከጋሻው ግን የበለጠባት የለም፡፡ ጋሻው የባንክ ቡኳን እሱ ጋር አስቀምጦ ገንዘብ ማውጣት ስትፈልግ ብቻ እንድታወጣ ለማንም ቤተሰብን ጨምሮ ገንዘብ እንዳትሰጥ አድርጓታል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በመስሪያ ቤት ማህበር ያለው መሆኑንና ለዚያ ቅድሚያ ክፍያ 30 ሺ ብር እንደሚያስፈልግ ነግሯት አውጥታ ሰጥታዋለች፡፡ ከዚህ በኋላ ቢቸገሩ 2 ዓመት ብቻ መሆኑን ገልፆላጽ አሁን ግን ቤት ተከራይተው ቢኖሩና ጋብቻቸውን በሚመቻቸው ጊዜ ቢያደርጉት የተሻለ መሆኑን አሳምኗታል፡፡ እመቤት ይህን ሁሉ ስታደርግ ያማከረችው አንድም ሰው እንደሌለ ስታውቅም ሁሉንም እርግፍ አድርጋ ተወቻቸው፡፡ ሁለት ክፍል ያላት አነስተኛ ቤት ተክለሃይማኖት አካባቢ ተከራዩ፡፡ ለቤቷ የሚያስፈልገውን ዕቃ በሙሉ ከ15 ሺ ብር በላይ አውጥታ የገዛችው እሷ ናት፡፡ በአንድ ግቢ ውስጥ ያለው ቤት ከርሷ ጋር ሌሎች ሁለት ተከራዮችን የያዘ ነው፡፡ መንደር ውስጥ ለውስጥ የገባ ቢሆንም ቤቱን ግን ሁለቱም ወደውታል፡፡ ጋሻውና እመቤት አብረው መኖር የጀመሩት በዚህ ሁኔታ ነው፡፡ የእመቤት ቤተሰቦች የልጃቸውን ከጉዞ መቅረትና ወንድ ወድዳ ቤት ተከራይታ መውጣት ፈፅሞ ያልደገፉት ነገር በመሆኑ በተለይ አባቷ አይኗን ሊያዩት እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል፡፡ እሷም በፍላጎቷ ማንም መግባት የሌለበት መሆኑን በመግለፅ ነው ከቤት የወጣችው፡፡ እናትየው ግን አላስችል ስላላቸው በተደጋጋሚ ጊዜ ደውለውላት አልፎ አልፎ አባቷ በሌሉ ጊዜ እየመጣች ታያቸዋለች፡፡ ጋሻው ቀን ቀን ወደ ስራ ብሎ ይሄድና ምሽት ላይ ይመታለ፡፡ አብሯት ያድራል፡፡ ህይወታቸውን መምራት ጀመሩ፡፡ ሁለት ወር ያህል ከኖሩ በኋላ ለምን እንደማይጋቡ ደጋግማ ትጠይቀው ነበር፡፡ በዚሁ ላይ አንድም ቀን ጓደኞቹንና እናቱን ሊያስተዋውቃት ያለማሰቡ ምክንያት ምን እንደሆነ ለማወቅ መጣር ጀመረች፡፡ ጋሻው እሷን ለሁሉም የሚያስተዋውቃት ድንገት ሁሉንም ሊያስደንቅ በሚችል ሁኔታ እንደሆነ እስከዚያው ግን አንድም ሰው እንዲያውቅበት የማይፈልገው ፍቅራቸው የሰው አፍ ውስጥ እንዳይገባ ፈልጎ መሆኑን በመንገር ይሸነግላት ነበር፡፡

በሌላ በኩል ያስቀመጠችው ገንዘብ በየጊዜው እየተመዘዘ ማለቁም እመቤትን አስጨንቋታል፡፡ ብዙ ገንዘብ ወጪ አድርጋ ቤቱን ማቋቋሟ ሳያንስ በሰበብ አስባቡ ገንዘብ እንድትሰጠው የሚጠይቃትን ጋሻውን ማስተናገድ በዝቶባታል፡፡ የወሰደው 30 ሺ ብር ሳያንስ የተለያዩ ምክንያቶች እየፈጠረ ገንዘብ ከባንክ እንድታወጣ ያደርጋት ነበር፡፡ የቤት አስቤዛ የምትገዛው እሷ ናት፡፡ እሱ ለጊዜው እናትና ታናናሾቹን እየረዳ በመሆኑ መስመር እስኪያሲዛቸው እንድትታገሰው ነግሯት ስለነበር ልትጫነው አልፈለገችም፡፡ ነገር ግን ሁልጊዜም ቤቱን እንድትሞላው- ሁሌም ደግሳ እንድትጠብቀው- ሁሉም ቢራና ወይን ከቤት እንዳይጠፋ መፈለጉ የልጅቷን የገንዘብ አቅም አመናመነው፡፡ ሶስት ወር ሲያልፋት ቢያንስ ቀለበት ማሰር እንዳለባቸው ትወተውተው ጀመረ፡፡ ለዚህም ምላሻ አላጣም፡፡ ቀለበት ማድረግ ብቻውን ዋጋ የሌለው መሆኑንና በቅርቡ ጋብቻቸውን መፈፀማቸው ላቀር ሌላ ወጪ መፍጠር የሌለባቸው መሆኑን ይነግራታል፡፡ ሁሌም ለምትጠይቀው ጥያቄ አሳማኝ ምላሽ አያጣምና በተቻለ መጠን እሱን ለማስቀየም ለማትፈልገው እመቤት ነገሩን በትዕግስትና በተስፋ መጠበቅ ብቻ ነበር አማራጯ፡፡

6 ወራት 1998 ጥቅምት

እመቤት ጓደኛዋን ፈለገቻት፡፡ በጋሻው የተነሳ የራቀቻትን ጋሻው ፈጽሞ እንዳታገኛት ብሎ ያለያያትን ጓደኛዋን ፈለገቻት፡፡ አሁን ነገሮች በፈለገችው መንገድ እየተጓዙ አይደሉም፡፡ በባንክ አካውንቷ የቀራት ገንዘብ 20 ሺ ብር ብቻ ነው፡፡ በ6 ወር ውስጥ ከ50 ሺ ብር በላይ አውጥታለች፡፡ ይህን ገንዘብ ለማግኘት 4 ዓመት ፈጅቶባታል፡፡ ጋሻው ገንዘብ የሚበቃው ሰው አይደለም፡፡ ተቃውሞ ስታቀርብ ሁሌም ያኮርፋል፡፡ ከእኔ ገንዘብሽን ታስቀድሚያለሽ ይታላል፡፡ በዚህ ትሳቀቃለች፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን የገንዘቡ ማለቅ አያሳስበውም፡፡ ህይወታቸው የሚመራው በርሷ ገንዘብ ሳይሆን በርሱ ደመወዝ እንደሆነ ደጋግሞ ቢነግራትም አንድም ቀን ሻሽ እንኳን ገዝቶላት አያውቅም፡፡ ውጪ ከርሷ ጋር ለመታየት ይፈራል፡፡ ጓደኞቹን፣ እናቱን አካባቢውን አያስተዋውቃትም፡፡ አብረው የሚወጡት ምሽት ላይ ሲሆን ብቻ ነው፡፡ ቀን ቀን ስራ እያለ ከእሁድ እስከ እሁድ ቤት አይገኝም፡፡ ምሽት ላይ ነው አብሯት የሚሆነው፡፡ እሷ ጋር ሲመጣ ሞባይሉን ያጠፋዋል፡፡ በየ15 ቀኑ ፊልድ እያለ ለአንድ ሳምንት ቆይቶ ይመለሳል፡፡ በእነዚያ ጊዜያት ሁሉ ስልኩ ይዘጋል፡፡ ከኔትዎርክ ውጪ ስለሆንኩ ነው ይላታል፡፡ አሁን አሁን ደግሞ ፀባዩ እየተለወጠ መጥቷል፡፡ እንዳትጸንስ ሁሌም ቢሆን ያስጠነቅቃታል፡፡ ይህ ሁሉ ነገር ልቧ ውስጥ ከፊል ጥርጣሬ እያሳደረባት ሲመጣ ጓደኛዋን ፈልጋ አግኝታ አዋየቻት፡፡

አሁን ከእንቅልፏ መባነን ጀመረች፡፡ ጓደኛዋ ሊሆን ይችላል ያለችውን ነገር ሁሉ ነገረቻት፡፡ ይህ ሰው ምናልባት እያጭበረበራት እንደሆነ ለማወቅ ማድረግ ያለባትን ሁሉ አስረዳቻት፡፡ በተለይ እሰራበታለሁ የሚልበትን መስሪያ ቤት በመጠየቅ እንድትተባበራት አማከረቻት፡፡ በዚህ መልኩ እመቤት በጋሻው ላይ ጥናት ማድረግ ጀመረች፡፡ አድርጋ የማታውቀውን ነገር ማድረግ ጀመረች፡፡ ጋሻው ለሽንት ከቤት ሲወጣ ቦርሳውን መበርበር ጀመረች፡፡ የመስሪያ ቤት መታወቂያ የለም፡፡ ነገር ግን የአንዲት ሴት ፎቶ ግራፍ አለ፡፡ በግምት 2 ዓመት የሚሆነው ወንድ ልጅ ያቀፈች ወጣት ነች፡፡ እመቤት ደነገጠች፡፡ ነገር ግን ምናልባት ዘመዱ ልትሆን ትችላለች ብላም አሰበች፡፡ የቀበሌ መታወቂያውን አየችው፡፡ ነዋሪነቱ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 18 ውስጥ መሆኑን ይናገራል፡፡ ከቤተሰቦቼ ጋር ጦር ኃይሎች እኖራለሁ ያለው ሀሰት መሆኑን ጠርጥራለች፡፡ ይህን አድራሻ በወረቀት ላይ መዘገበችና ያዘች፡፡ በማግስቱ ለጓደኛዋ ነገረቻት፡፡ ቀስ በቀስ ጋሻው እውነተኛ ሰው እንዳልሆነ ለመረዳት የቻለችበትን መረጃዎች አገነች፡፡ ስልኩን ሳያይ አውጥታ በውስጡ የተቀዱትን የቪዲዮ ምስሎች ተመለከተች፡፡ በፎቶ ግራፍ ላያ ያየቻትን ሴት አይነት ሴት አለች፡፡ አንድ ህፃን ልጅ በተደጋጋሚ ጊዜ ተቀርጿል፡፡ ደነገጠች፡፡

ጓደኛዋ ይህን ካወቀች በኋላ እመቤት ጋሻውን ማውጣጣት እንዳለባት አሰበችና ተመካከሩ፡፡ አንደ ቀን ጋሻውን ‹‹ለምን ከሰዎች ጋር እንደማታስተዋውቀኝ ገብቶኛል፡፡ ልጅና ትዳር እንዳለህ ደርሼበታለሁ፡፡ ስለዚህ ገንዘቤን መልስልኝ›› እንድትለው ነገረቻት፡፡

ህዳር 17/1998

ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ላይ በር ተንኳኳ፡፡ ቀኑን ሙሉ ቤት ተቀምጣ በሃሳብ ስትብሰከሰክ ለዋለችው ለእመቤት ይህ ምሽት የመጨረሻ ነው፡፡ ውስጧ ተበሳጭቷል፡፡ የተለየ ስሜት ተሰምቷታል፡፡ የመከዳት ስሜት ተሰምቷታል፡፡ በሀሰት የሚሸነግላት፣ የሚያታልላት ልቧን በሰረቀበት የማባበያና የማሳመኛ ቃሉ ሌላ እንዳታስብ አድርጎ አዕምሮዋን የጋረደባት እጅግ ስለምትወደውና ሌላ ለማሰብ ራሷን ስላላዘጋጀች ነበር፡፡ አሁን ግን ቆም ብላ ስታስብ የሆነው ሁሉ ተረት ተረት መስሎ ታያት፡፡ ስለዚህ ዛሬ እውነቱን የምታውቅበት ዕለት ነው፡፡ ጋሻው ወደ ቤት ገባ፡፡ እንደተለመደው እቅፍ አድርጎ ሳማት፡፡ መጠት መጠጥ ሸቷታል፡፡ ለምን እንደመጣ ጠየቀችው፡፡ የሆኑ ከውጭ የመጡ የመስሪያ ቤት እንግዶችን ሲያስተናግድ ቢራ መጠጣቱን ነገራትት፡ ከዚህ በኋላ ነበር ጦርነቱ የተጀመረው፡፡

ስራ የሌለው መሆኑንና እስካሁንም የተጫወተባት እንደሚበቃ ነገር ግን የወሰደባትን ገንዘብ ሁሉ እንዲመልስላት ካልሆነ ግን ለሚስቱ እንደምትደውልላት አስጠነቀቀችው፡፡ ቱግ አለ፡፡ ይህ ወሬ ያወራላት ሀሰተኛ እነርሱን ለመለያየት የፈለገ ሰው መሆኑን ነገራት፡፡ ነገር ግን እራሷ ማወቋንና ከሞባይሉ ውስጥ ያየችውን ቪዲዮ እንዲሁም ቦርሳው ውስጥ ያየችውን ፎቶግራፍ ሁሉ ነገረችው፡፡ ቦርሳውን ከፍቶ እንዲያሳያትና ሞባይሉንም አውጥቶ ቪዲዮውን የማን እንደሆነ እንዲገልፅላት ጠየቀችው፡፡ ተቆጣ፡፡ የእርሱን ሞባይልና ቦርሳ ለመጎርጎር ፈፅሞ መብት የሌላት መሆኑንና ቢያደርገውም የሚያገባት ነገር የሌለ መሆኑን ገለፀላት፡፡ ፀብ ተቀሰቀሰ፡፡ እመቤት ህይወቷን ማበላሸቱንና ከዚህ በኋላ ምንም አይነት ግንኙነት እንዲኖራት የማትፈልግ መሆኑን ነግራ ሌላ ግንኙነት እንዳለው ያንንም የሰራትን ሄዳ በመንገር እንደምትበጠብጥበት ስትነግረው አነቃት፡፡ መታገል ጀመሩ፡፡
እመቤት ራሷን መቆጣጠር ተስኗት መጮኽ ጀመረች፡፡ ልትቧጭረው ፈለገች፡፡ እሱም ይደብድባት ነበር፡፡ በመጨረሻ ላይ ባላሰበችው ሁኔታ አጠገቧ ያገኘችውን የኒኬል ብርጭቆ ወርውራ ስትመታው እጇን ጠምዝዞ ጣላት፡፡ አጠገቡ ያገኘውን የሽንኩርት መክተፊያ ቢላዋ ሲይዝ ልትቀማው ታገለችው፡፡ በጩኸት ሰው መጣራት ጀመረች፡፡ አፏን አፍኖ ወደ ታች የሰነዘረው ቢላዋ ዘወር ስትል ትከሻዋ ላይ ተሰካ፡፡ ጮኸችና ወደቀች፡፤ ግርግሩን የሰሙ ሰዎች ተሯሩጠው ወደበሩ ሲደርሱና እሱ ከፍቶ ሲወጣ አንድ ሆነ፡፡ ድንገት መሬት ላይ ወድቃ በደም ተበክላ ያዩዋት የቤቱ አከራይ ‹‹ገድሏታል›› ብለው ሲጮኹ ጋሻው ከአካባቢው ተፈትልኮ ጠፋ፡፡ ሰዎች በዚህ ምሽት ተሯሩጠው ቢፈልጉትም ሊያገኙት አልቻሉም፡፡ እመቤትን ከወደቀችበት አንስተው በኮንትራት ታክሲ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወሰዷት፡፡ ሐኪሞች በድንገተኛ ክፍል ከእጇ ላይ የሚፈሰው ደም ከቆመላት በኋላ አልጋ አስያዟት፡፡ ህይወቷ ተርፏል፡፡

ከሳምንት በኋላ
ፖሊስ በደረሰው መረጃ መሰረት ባደረገው ማጣራት ጋሻው የሚኖርበትን አድራሻ ከእመቤት ጓደኛ አግኝቷል፡፡ በስልኩ ሲደወል ስልኩ የተዘጋ መሆኑን ቢገልፅም ፖሊስ ግን የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ ይዞ ያለበት በአድራሻ ድረስ ሄዶ ቤቱን አገኘው፡፡ የሚኖርበት ቤት ውስጥ አያቱ አሉ፡፡ ሰሞኑን መጥቶ እንደማያውቅ የሄደበትን እንደማያውቁ ተናገሩ፡፡ ጋሻው ስራ የለውም፡፡ አልፎ አልፎ ደላልነት ይሞክራል፡፡ ከአንዲት ሴት ወልዶ እሷ አሁን አረብ አገር እየሰራች ነው፡፡ ተጋብተው ይኖሩ የነበረ ሲሆን እሷ ወደ ውጭ ስትሄድ ነው ወደ አያቱ ቤት የተመለሰው፡፡ ልጁን እያሳደገ ነው፡፡ ልጅቷ ከዓመት በኋላ ተመልሳ ትመጣለች፡፡ ህጋዊ የጋብቻ ወረቀትም ነበረው፡፡

ከ15 ቀናት ክትትል በኋላ ፖሊስ በጥቆማ ምሽት ላይ ወደ ቤቱ ሲመጣ ጋሻውን በቁጥጥር ስር አዋለው፡፡ በወቅቱም የእመቤትን የባንክ ደብተር ካስቀመጠበት እንዲያመጣ አደረገው፡፡ በመግደል ሙከራ ወንጀል ክስ የቀረበበት ጋሻው ከዚህ በተጨማሪም በማታለልና በማጭበርበር የሰው ገንዘብን ለራስ ጥቅም በማዋል ተከሷል፡፡ በህይወት የተረፈችው እመቤት ጋሻው እስር ቤት ከገባ በኋላ የሆነውን ነገር ሁሉ አረብ አገር ላለችው ሚስቱ ስልኳን ፈላልጋ ደውላ ነግራታለች፡፡ ልጅቷ ባለችበት ሆና ጋሻው የሚባል ባል እንደሌላትና አገሯም እንደማትመጣ ልጇን ግን እንደምትረዳ ለቤተሰቦቿ ነግራቸዋለች፡፡ ቤተሰቦቿም የተፈፀመውን ታሪክ አውቀዋል፡፡ ጋሻው በፈፀመው ወንጀል እስር ቤት ቢገባም እመቤት ከአካል ጉዳት ባሻገር የማይጠገን የህሊናና የሞራል ጉዳት ደርሶባታል፡፡ ከቤተሰቦቿ ጋር አብራ መኖር ብትጀምርም የጥፋተኝነት ስሜቱ ጠንቶበት ነበርና ከጓደኛዋ ጋር መኖር መርጣለች፡፡ በፍርድ ቤት የጋሻው ጉዳይ በመታየት ላይ ሳለ ነበር ወደ ውጭ ሃገር የተመለሰችው፡፡ የቀራትን 20 ሺ ለዚሁ ፕሮሰስ አውላ ሌሎች ብዙ ዓመታትን ጉልበቷን እየገበረች ብር ለማጠራቀም ይህችን ሀገር ጥላ ሄደች፡፡ አምሳለ እመቤት ተመልሳ ወደዚህች አገር ትመለሳለች የሚል ተስፋ የላትም፡፡ ምናልባትም ዛሬም ድረስ ይህችን አገር አላየቻት ይሆናል፡፡ አጭበርባሪው ግለሰብ ግን በወህኒ ቤት ለሰራቸው ተደራራቢ ወንጀሎች ፍርዱን እየተቀበለ ነው፡፡ ምናልባት ሚስቱ ስትመጣ በጋብቻ ላይ በመማገጥ ወንጀል ክስ ልትመሰርትበት ወይም ህሊናው ይቅጣው ብላ ልትተወው ትችል ይሆናል፡፡ ያ ታሪክ ዛሬ ቀላል ቢመስልም በተጎጂዎቹ ሴቶች ላይ የጣለው ጠባሳ ግን ምናልባትም የህይወት ዘመናቸውን ሙሉ ይከተላቸው ይሆናል፡፡

ከአሜሪካ መልስ –ከተስፋዬ ገ/አብ

$
0
0

በታዋቂው የታሪክ ምሁር በፕሮፌሰር መሃመድ ሃሰን (የOSA አመራር አባል) እንዲሁም በመጫና ቱለማ ማህበር ጋባዥነት በአሜሪካ ያደረግሁትን የሶስት ወራት ቆይታ አጠናቅቄ ወደ ኤርትራ ተመልሻለሁ።

(ተስፋዬ ገብረአብ)

(ተስፋዬ ገብረአብ)


ለፕሮፌሰር መሃመድ፣ ለመጫና ቱለማ ማህበር አባላት፣ እንዲሁም በተዘዋወርኩባቸው የአሜሪካ ግዛቶች፣ በዋሽንግተን ዲሲ፣ በኒውዮርክ፣ በላስቬጋስና በሚኒሶታ የደመቀ ወንድማዊ አቀባበል ላደረጉልኝ፣ በክብር ላስተናገዱኝ ኦሮሞ ወገኖች ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋናዬን በይፋ ማቅረብ ተገቢ ሆኖ አጊኝቼዋለሁ።

በተጨማሪ የዋሽንግተን ዲሲ የኤርትራ ኮሚኒቲ አባላት በተለያዩ ፕሮግራሞች ከኔ ጋር ባደረጉት ልዩ ቆይታ በእጅጉ ተደስቻለሁ። በአጠቃላይ ከአፍሪቃ ቀንድ ዜጎች ጋር በአካባቢያችን የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ፣ እንዲሁም በስነፅሁፍ ነክ ርእሰ ጉዳዮች፣ ካደረግሁዋቸው ውይይቶች እጅግ ብዙ ትምህርት ቀስሜያለሁ። በመሆኑም ጉዞዬ ሙሉ በሙሉ የተሳካ ነበር።

• • •
ከአሜሪካ መልስ እነሆ! በህግ ኦሮሞ ሆኛለሁ።

ኦሮሞ መሆን “ኢትዮጵያዊ መሆን” ማለት ግን አይደለም። ወደፊት የኦሮሞ ህዝብ ስለማንነቱ በነፃነት ሲወስን ያን ጊዜ የሚታይ ይሆናል። ኢትዮጵያዊነትን በመተው ኦሮሞ ብቻ ሆኖ መቆየት እንደሚቻል ግን ቀደም ሲል በሞጋሳ ባህል ኦሮሞነትን ከወሰዱ ግለሰቦች ተረድቻለሁ። አንትሮፓሎጂስት ቦኒ ሆሎኮም፣ (ቃበኔ) እና አስመሮም ለገሰ (ሃዩ) ሊጠቀሱ ይችላሉ። በመሰረቱ ለገዳ ገብረአብ የሚያስፈልገው ትልቁ ጉዳይ እውቅናው ነበር። ግማሽ የህይወቱን ክፍል የታገለለት አላማ በመጨረሻ በኦሮሞ ህዝብ ፊት ዋጋና ሞገስ ማግኘቱ በትክክለኛው መስመር ላይ ሲጓዝ እንደቆየ ማረጋገጫ ሆኖለታል።
እንግዲህ በሞጋሳ ስርአት መሰረት ኦሮሞነትን በኩራት የተቀበልኩ በመሆኑ በኦሮሚያና በአካባቢያችን ጉዳዮች ላይ የመፃፍ ብቻ ሳይሆን፣ የመሳተፍ ጭምር ግዴታ አለብኝ። ከዚያም ባሻገር ትግሉ ሲጠናቀቅ፣በመጪው ዘመን ገዳ ገብረአብ ከገላን እስከ ከረዩ በተዘረጋው ጥንታዊ የኦሮሞ ግዛት ላይ ለአስተዳዳሪነት ሊወዳደር ይቻለዋል። የኦሮሞ ህዝብ ራሱን በራሱ ማስተዳደር ሲጀምር ገዳ ገብረአብ ከየረር እስከ ጨፌ ዶንሳ በተዘረጋው ነፃ ሁዳድ ላይ የበቆሎ እርሻ ስራ ሊሰራ፣ በጎችና ዶሮዎችን ሊያረባ፣ ሰፋፊ መስኮቶች ያሉት ገልመ ገዳ ሊገነባ፣ በዙሪያውም ቀያይ ቅጠሎች ያላቸውን ዛፎች ሊተክል አሳብ አለው። ይህ አሳብ ህልም አይደለም። ነገ ይፈፀማል።

ዋሽንግተን ዲሲ ላይ ሰአታት በወሰደ ባህላዊ ስነስርአት ኦሮሞ መሆኔ ሲረጋገጥ አባቴ እንዲሆኑ በጉባኤው የተመረጡት ኦቦ ሉቤ የሚከተለውን ተናግረው ነበር፣

“ከዚህች ቀን ጀምሮ ገዳ ገብረአብ በህግ የኛ ሆኖአል። ገዳ ላይ የሚደርስ ጥቃት ካለ ከጎኑ እንቆማለን። ገዳን የነካ እኛን እንደነካ ይቆጠራል።”
ይህ ሲነገር እልልታና ጭብጨባ የዋሽንግተን ዲሲን መልካ አደመቀው። በአካባቢው የነበሩ ነጭ አሜሪካውያን ምን እየተካሄደ እንዳለ ባለማወቃቸው በመደነቅ ያዩ ነበር። እኛ ግን ከ2800 አመታት በፊት ጀምሮ በቱለማም ሆነ በመጫ ሰዎች ይካሄድ የነበረውን ስርአት በመፈፀም ላይ ነበርን። የገላን አራተኛ ልጅ፣ የሃንዳ፣ የዳኩ እና የኢሉ አባት የአድአ ጥቁር አፈር እንደመሆኔ እኔም አንገቴን ጎንበስ በማድረግ ምስጋናዬን ገለፅኩ።
ኦሮሞ መሆኔ እንደተሰማ ከጠላቶቼ አንዱ ጎረቤቱ ለሆነ ኦሮሞ የተናገረውን በተዘዋዋሪ ሰማሁ፣
“የኢትዮጵያን አንድነት እንዲያተራምስ ህጋዊ እውቅና ሰጣችሁት። አዘንኩባችሁ!!”

• • •
ርግጥ ነው “ኦሮሞ” የሚለው ቃል ሲነሳ የሚረበሹ ወገኖች አሉ። ኦሮሞዎች “ኦሮሞ” የሚለውን ቃል እንዳያነሱ የማሸማቀቅ ተፅእኖ ለማድረግ አሁንም ድረስ ይሞከራል። በመኪናው ውስጥ የኦሮምኛ ዘፈን ከፍቶ የሚሄድ ሰው ካጋጠማቸው፣ “ይሄ ዘረኛ!” ይሉታል። ታክሲ ውስጥ ኦሮምኛ የሚናገር ሰው ሲሰሙ ተገላምጠው ያዩታል። ከደብተሮቻቸው በወረሱት አሸማቃቂና አስፀያፊ ስድብ ኦሮሞ ኦሮሞነቱን እንዲሸሽ ለረጅም ዘመናት ጥረት አድርገው ሳይሳካላቸው ቀረ። በርግጥ እነዚህ ሰዎች አማሮች አይደሉም። “ኢትዮ- አማሮች” ተብለው ይታወቃሉ። በኢትዮጵያዊነት እና በአንድነት ስም ለአንድ ወገን መብት መከበር የሚታገሉ ናቸው። እነዚህን ወገኖች በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ድብቅ አጀንዳቸውን መግፈፍ ያስፈልጋል። በዚህ ዘመን ተሸፋፍነውመጓዝእንደማይችሉ መንገር ያስፈልጋል። ወያኔ የኦሮሞን ህዝብ መብት የረገጠ አፋኝ ቡድን ነው። ኢትዮ አማሮች ደግሞ ከወያኔ በከፋ ደረጃ የኦሮሞን ህዝብ መብቶች ለማፈን ጊዜ የሚጠብቁ መሆናቸውን የኦሮሞ ህዝብ ጠንቅቆ ሊረዳው ይገባል። በመሆኑም ከወያኔ መውደቅ ቀጥሎ የኦሮሞ ህዝብ ከባድ ፈተና የሚገጥመው ከእነዚሁ እላዩ ላይ መጥተው ቁጭ ካሉበት ሰፋሪዎች ነው።

የአሜሪካ ቆይታዬን በተሳካ ሁኔታ አጠናቅቄ ቀጣዩን ዳጎስ ያለ “ታሪክ ቀመስ ልቦለድ ድርሰት” ለመፃፍ ወደ ኤርትራ ተመልሻለሁ። አስመራ ባረፍኩ በሶስተኛው እለት ከOLF ሰዎች ጋር ጥቂት የራት ላይ ቆይታ አድርገን ነበር።ዳውድ ኢብሳ ባደረገው አጭር ንግግር፣

“የኦሮሞን ጉዳይ በማንሳቱ ጥቃት የደረሰበት ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ የመጀመሪያው አይደለም። የመጨረሻው ላይሆንም ይችላል።” ሲል ተናግሮአል።

እኔም አንድ ነጥብ አንስቼያለሁ፣
“መጪው ዘመን የኦሮሞ ህዝብ ዘመን ነው።” ካልኩ በሁዋላ አከልኩበት፣ “…የኦሮሞ ህዝብ ጭቆናን በጭቆና የመመለስ ባህል ስለሌለው፣ በመጪው ዘመን በማንኛውም ጊዜ በሚጀምረው የኦሮሞ ህዝብ ዘመነ መንግስት አካባቢያችን የተሻለ ሰላምና ፍትህ እንደሚያገኝ ተስፋ አለኝ።”

• • •
እነሆ! ወደ ኤርትራ ከተመለስኩ ሳምንት ሞላኝ።

ትናንት ወደ ምፅዋ ሄጄ ነበር። ምፅዋ የሚያስኬድ ምንም ጉዳይ አልነበረኝም።የተጓዝኩት ለቀይባህር ደረት የሞቀ ሰላምታ ለማቅረብ ብቻ ነበር። የቀይባህር የምሽት ማእበል ናፍቆኝ ነበር። የምፅዋ ሙቀት በጣም ናፍቆኝ ነበር። የጀበና ቡና እና ፈንዲሻ – ባህሩ ዳርቻ ናፍቆኝ ነበር።

ህዳር2፣ 2014ዳህላክ ሆቴል ስደርስ ሊመሽ ምንም አልቀረውም። በቅፅል ስሙ ባዙቃ ብለን የምንጠራው፣ የOLF ታጋይ ማምሻውን ወዳለሁበት ብቅ ብሎ ተገናኝተን ነበር። ከሰላምታ በፊት እንዲህ አለኝ፣
“ከበፍቃዱ ሞረዳ ጋር ያደረግኸውን ቃለመጠይቅ ዛሬ ማለዳ ኦሜን (OMN) ቴሌቪዥን ላይ ተከታትዬው ነበር። ጥሩ ነበር። በጣም ጥሩ ነበር። ብቻ በአንድ ነገር ቅር ብሎናል። ‘የወሎ አማሮች’ ስትል ሰማንህ። ምን ለማለት ፈልገህ ነው? ከመቼ ወዲህ ነው ወሎ የአማራ የሆነው?”

•••
ባህሩ ዳር ቁጭ ብለን አመሸን…
ሰማዩ በሩቅ ቀልቶ ታየን። ብዙም ሳይቆይ መሸ። ጨርሶ ጨለመ። ባህሩን ተሻግሮ በርቀት ብርሃን አየሁ። ብልጭ ብልጭ ይላል። የሳዑዲአረቢያ ዳርቻ አይመስለኝም። እንዲህ በቅርብ ርቀት ሊታይ አይችልም። በርግጥ አሰብ ባህሩ ዳርቻ ቁጭ ያለ የየመንን የሌሊት መብራት ማየት እንደሚችል ሰምቻለሁ። ከዚህ ከምፅዋ ግን የሳዑዲ አረቢያ ዳርቻሊታይ አትችልም። በሩቅ የማየው ብርሃን ‘ምን እንደሆነ’ ባዙቃን ጠየቅሁት፣
“ገደም ነው።” ሲል ነገረኝ።

“ገደም” ምን እንደሆነ አላወቅሁም። “ገደም ምንድነው?” ብዬ መጠየቅ ግን አልፈለግሁም። በነገው እለት ገደም ምን እንደሆነ ለማወቅ ብርሃን ወዳየሁበት አቅጣጫ በታንኳ እጓዛለሁ…

Health: ሱስና መፍትሄዎቹ

$
0
0

አንድ ስኒ ቡና ለንቃት ሁለትና ሶስት ድብን ብሎ በመተኛት የካፌይን ተፅዕኖ ሲገለፅ

በተለያዩ አጋጣሚዎች ስራ፣ ጥናትንና በአጠቃላይ ለነቃ ውሎ ስንል ካፌይን ብለን የምንጠራውን ኬሚካል የያዙ መጠጦችንና ምግቦችን እንወስዳለን፡፡ በተለይም የዚህ ኬሚካል በብዛት መገኛ የሆኑትና በደከመንና በዛልን ወቅት ከድብርትና ከዱካክ ወጥተን ነቃ እንድንል የምንጠጣቸው ቡና፣ ሻይና የተለያዩ ለስላሳ መጠጦች ዋነኛ ተጠቃች ናቸው፡፡ ካፌይን አዕምሮን የሚያነቃቃ ሲሆን ከላይ ከጠቀስናቸው መጠጦች በተጨማሪ በሌሎች መግቦች ውስጥ ለምሳሌ በብስኩቶችና በቸኮሌቶች ውስጥ እንደዚሁም በአንዳንድ መድኃኒቶች (ለምሳሌ በራስ ምታት መድሃኒቶችና ማስታገሻዎች) ውስጥ በሰፊው የሚገኝ ነው፡፡ በአገራችንም በተለያየ መልኩ በሚሊዮን በሚቆጠሩ ሰዎች የሚወሰድ ነው፡፡ በብዙ ሰዎች በመወሰዱና በመለመዱም በተለያዩ ባለስልጣናትና የሃይማኖት መሪዎች ዘንድ ሳይቀር በ‹‹እፅ›› መልክ የሚወሰድም ነው፡፡ ነገር ግን ካፌይን መውሰድና ሱስ ውስጥ መግባት ከጤና ጋር ተያይዞ የሚመጡ ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል፡፡
ethiopian coffee
አንድ ስኒ ቡና ከ100 እስከ 150 ሚሊ ግራም ካፌይን በውስጡ ይይዛል፡፡ ሻይ የዚህን ሲሶ ያህል ካፌይን ሲኖው፣ በአንዳንድ መድሃኒቶች ይህንን ያህል ካፌይን የመገኘት አጋጣሚም ሊኖር ይችላል፡፡ በለስላሳ መጠጦች፣ በጣፋጭ ከረሜላዎችና ቸኮሌቶች ውስጥ እንደዚሁም በብስኩቶችና በሻይ ውስጥም በብዛት መኖሩ ህፃናት ልጆችም ሳይቀሩ በቀላሉ ሊወስዱት ይችላሉ፡፡
በዓለም ዙሪያ በአማካይ በቀን ውስጥ ከ80 ሚሊ ግራም በላይ ካፌይን በየቀኑ ይወሰዳል ተብሎ ይገመታል፡፡ ከካፌይን ጋር የተያያዙ አራት አይነት የጤና ችግሮች አሉ፡፡

1. የካፌይን ስካር (ኢንቶክሲኬሽን)
ይህ ስካር የሚጀምረው ከ250 ሚ.ግ በላይ ካፌይን ከተወሰደ በኋላ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዘው የሚታዩ ምልክቶች ጭንቀት፣ የህሊና መረበሽ፣ መቁነጥነጥ፣ መነጫነጭ፣ ማቅለሽለሽ፣ ማላብ፣ የሆድ መረበሽ፣ የሽንት መብዛት፣ እንቅልፍ ማጣትና በእግርና በእጅ ጣቶች ላይ የመወረር አይነት ስሜቶች መፈጠር ናቸው፡፡ በዚህ ጊዜ የተወሰደው ካፌይን ከ1000 ሚ.ግ በላይ ከሆነ የአፍ መኮላተፍ፣ የሃሳብ መደነጋገር፣ የልብ ትርታ መዛባት፣ ወፈፍ ማድረግ፣ የሌለና የማይታይ ብርሃን መታየት ሊከተሉ ይችላሉ፡፡ የካፌይን ብዛቱ ከ10,000 ሚሊ ግራም (10 ግራም) በላይ ካለፈ ግን ድንገተኛ ሞት ሁሉ ሊከተል ይችላል፡፡

2. ካፌይን ሳይወሰድ ሲቀር የሚከሰት ህመም
በዚህ ጊዜ የህመሙ አይነትና መጠን ከሰው ሰው እንደሚወሰደውና እንዳስለመዱት ብዛትና የልምድ ጊዜ እርዝመት ይለያያል፡፡ የተለመደው ካፌይን ሲቀር ከሚታዩ ምልክቶች መካከል ራስ ምታት፣ ጭንቀት ወይም መደበት፣ ድካም ወይም መፍዘዝ፣ ማቅለሽለሽ ወይም ማስታወክ ሊከተሉ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ካፌይኑ ከቀረ ከ12 እስከ 24 ሰዓታት ውጥ የሚጀምሩ ሲሆን በሁለተኛው ቀን የሚብሱ ነገር ግን በአንድ ሳምንት ውስጥ ተመልሰው የሚጠፉ ናቸው፡፡

3. የእንቅልፍ መቃወስና ጥልቅ የሆነ ጭንቀት
መረበሽ፣ መነጫነጭ፣ መቁነጥነጥ ወይም በአንድ ቦታ ረጋ ብሎ አለመቀመጥን ሊያመጣ ይችላል፡፡ በተለይም የመርበትበትና በሆነው ባልሆነው መደንገጥ ያለባቸው ሰዎች ካፌይን በብዛት ከወሰዱ በኋላ በሽታው ሊነሳባቸው ይችላል፡፡ ስለዚህም በተቻለ መጠን ህመማቸው እንዳያገረሽባቸው ብዙ ካፌዬን መውሰዳቸውን መቀነስ አለባቸው፡፡ ይህ ካልሆነ ደግሞ ትልቅ ጭንቀት ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ፡፡
በእንቅልፍ ላይ የሚያመጣውን ለውጥ ስናይ ደግሞ ቶሎ እንቅልፍ እንዳይመጣ ካደረገ በኋላ በቀጣይነት ለረዥም ጊዜ መተኛት አለመቻልና በማለዳ ከእንቅልፍ መንቃትን የሚያስከትላቸው ተፅዕኖዎች ናቸው፡፡

የመፍትሄ እርምጃዎች
የካፌይን አጠቃቀምን ለመቀነስ ወይም እስከ መጨረሻው ለማቆም የመጀመሪያ እርምጃው ምን ያህል ካፌይን በቀን እንደሚወሰድ እና በምን አይነት መንገድ እንደተወሰዱ (በመጠጥ፣ በምግብ፣ በመድሃኒት…ወዘተ) እንደሚወስዱ ለይቶ ማወቅ፡፡
ከዚህ በኋላ በአንድ ጊዜ ሳይሆን ቀስ በቀስ የካፌይን አወሳሰዱን በመቀነስ በሳምንታት ውስጥ የሚፈለገው የተሻለ የመፍትሄ ደረጃ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡ ከእነዚህ ጋር አብሮ ካፌይን የሌላቸውን መጠጦችንና ምግቦችን ለይቶ አውቆ እነዚህኑ በምትክ መውሰድን ልማድ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡ ካፌይን መውሰድ በድንገት በሚቆምበት ጊዜ የሚከተሉትን ህመሞችንና የድብርት ስሜቶች ሲከሰቱ ማስታገሻ መድሃኒቶችን መውሰድ የተሻለ አማራጭ ነው፡፡
ለዚህም ነው አንድ ስኒ ቡና ጥሩ ንቃትን ለመፍጠር ያስችላል፡፡ ነገር ግን ሁለት ሶስት እያልን ስንደጋግም የአንጎላችን የመላመድ ብቃት እየጨመረ ይመጣና በንቃት ከመቆየት ይልቅ ድብን ወዳለ የእንቅልፍ ዓለም ውስጥም ያስገባል፡፡ ይህም የካፌይን ተፅዕኖ ተቃራኒ በሆነ መልኩ የሚፈፅመው ድርጊትም ጭምር ነው፡፡ በአጠቃላይ የካፌይን አጠቃቀማችንን ከምንወዳቸው ምግቦችና መጠጦች አንፃር መጠኑን በመቆጣጠር መቀነስ ሲልም እስከመተው ደረጃ መድረስ እንችላለን፡፡

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live