Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ማዕከላዊ የሚታሰሩት የጋምቤላ ክልል ነዋሪዎች ቁጥር አሻቅቧል * በርካታ የጋምቤላ ክልል ነዋሪዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል

$
0
0

የህወሓት/ኢህአዴግ ባለስልጣናት በኢንቨስትመንት ስም የጋምቤላን ክልል ነዋሪዎች እያፈናቀሉ በያዙት መሬት ምክንያት እንደተቀሰቀሰ የሚነገርለትና ለወራት በዘለቀው ግጭት ተሳታፊ ናቸው የተባሉ በርካታ የጋምቤላ ክልል ነዋሪዎች ዛሬ ጥቅምት 20/2007 ዓ.ም በአራዳ ምድብ ችሎት መቅረባቸው ታወቀ፡፡

ነዋሪዎቹ ከጋምቤላ ክልል ወደ ማዕከላዊ ከመጡ በኋላ ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበዋል፡፡ ዜጎች ወደ ችሎቱ በሁለት የፖሊስ አውቶቡሶች የመጡ ሲሆን በቁጥር ቢያንስ 50 እንደሚደርሱ ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ችሎቱ በዝግ እንደተካሄደም ለማወቅ ተችሏል፡፡

news
ከጋምቤላ ክልል የመጡት ዜጎች በአራዳ ምድብ ችሎት በቀረቡበት ተመሳሳይ ሰዓት የሸዋስ አሰፋ፣ ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሺና አብርሃ ደስታ የሚቀርቡ በመሆኑ በዚህ ችሎት ለመታደም የሄደው ህዝብ ከጋምቤላ የመጡት ዜጎች ላይ በተደረገው ጥብቅ ጥበቃ ምክንያት ከፍተኛ ፍተሻ እንደተደረገበት በቦታው የተገኘው የነገረ ኢትዮጵያ ዘጋቢ አረጋግጧል፡፡ በቦታውም ለጥበቃ የፌደራል ፖሊስ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስና የማረሚያ ቤት ፖሊስ እንደተገኙም ታውቋል፡፡ ዛሬ አራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡት የጋምቤላ ክልል ነዋሪች መቼ ወደማዕከላዊ እንደመጡ የታወቀ ነገር የለም፡፡

በሌላ በኩል ትናንት ጥቅምት 19/ 2007 ዓ.ም ወደ ማታ አካባቢ ጋምቤላ ክልል ውስጥ በተፈጠረውና ለወራትም የበርካታ ሰው ህይወት ከጠፋበት ግጭት ጋር በተያያዘ በርካታ ዜጎች በአውቶቡስ ተጭነው ወደ ማዕከላዊ መግባታቸውን የአይን እማኞች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ወደ ማዕከላዊ ከመጡት መካከል የአካባቢው ባለስልጣናትም እንደሚገኙበት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች አክለው ገልጸዋል፡፡

በዛሬው ዕለት ችሎት የቀረቡትንና በትናንትናው ዕለት ወደ ማዕከላዊ የመጡን ጨምሮ ጋምቤላ ክልል ውስጥ በተፈጠረው ግጭት ምክንያት ማዕከላዊ የሚታሰሩት ዜጎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሸቀበ መሆኑም ተገልጾአል፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ ለአንባቢዎቿ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማቅረብ ጥረት ታደርጋለች፡፡


Health: ስኳር ህሙማን ለምን ስኳር ይከለከላሉ?

$
0
0

በቅርብ ጊዜያቶች ስለ ስኳር በሽታ ይቀርቡ የነበሩ መረጃዎችን አንብቤያለሁ፡፡ በአጠቃላይ ከተዘረዘሩት ውስጥ በተለየ ሁኔታ ስለ ሃይፖግላይሴሚያ ማብራሪያ እፈልጋለሁ፡፡ ይኸውም በሽታው ሃይፖግላይሴሚያ፣ በደም ውስጥ የስኳር ማነስ ነውና ለምን የስኳር ምግቦችን በሽተኛው እንደሚከለከል አልገባኝም፡፡ እኔ የስኳር በሽታ ተጠቂ ብሆንም ችግሬ የሃይፖግላይሴሚያ (ተረፈ ስኳር) እንዳልሆነ ያወቁ ሰዎች ወይም የነገርኳቸው ጣፋጭ ብቀምስ ምንም እንደማልሆን ይገልፁልኛል፡፡ እንዳሉትም በመጠኑ ሳደርግ ችግሩ ይብስብኛል፡፡ ሆኖም የእግር እንቅስቃሴ ከማድረጌ በቀር የተሰጠኝ ክኒን ባለመኖሩ አላዋቂዎችን ማሳመን ከብዶኛል፡፡ ለማንኛውም ግን ሃይፖግላይሰሚያ ለሃይፐርግላይሴሚያ ቀዳሚ ምልክት ላይሆን የሚችልበት ሁኔታ ካለና ማብራሪያ ብትሰጡኝ እወዳለሁ፡፡

ask your doctor

ውድ የአምዳችን ተከታታይ ነፃነት ጥያቄህን ግልፅ በማድረግ አንተ የስኳር ህመምተኛ መሆንህን ነገር ግን ሃይፖግላይሴሚያም (የስኳር ማነስ) ሆነ ሃይፐርግላይሴሚያ (ተረፈ ስኳር) የሌለብህ ቢሆንም ስለ ሁለቱ ማወቅ ግን ትፈልጋለህ፡፡ በአጭሩ ለመግለፅ ያክል በሰውነታችን ውስጥ ትክክለኛ የስኳር መጠን ከ70 ሚ.ግ-110 ሚ.ግ በአንድ ሚሊ ሊትር ደም ውስጥ ይገኛል፡፡
ነገር ግን የስኳሩ መጠን ከ70 ካነሰ አነሰ ስኳር (አይፖግላይሴሚያ) ከ110 ከበለጠ ደግሞ ተረፈ ስኳር (ሃይፐርግላይሴሚያ) ይባላል፡፡ ብዙውን ጊዜ ሃይፐርግላይሴሚያ የምንለው የስኳር ልክ ከሌሎች ምልክቶች ጋር ተደምሮ የስኳር በሽታ ተብሎ ይጠራል፡፡ ከዚህ በተረፈ ሃይፖግላይሴሚያ የስኳር በሽ በህክምና ጊዜ የስኳር መጠናቸውን ለመቀነስ የሚወስዱት መድሃኒት ከበዛ ወይም መድሃኒት እየወሰዱ ነገር ግን በተገቢው ሰዓት ምግብ ካልወሰዱ የደም ስኳራቸው የሚያንስበት ሁኔታ ነው እንጂ ራሱን የቻለ በሽታ አይደለም፡፡ በዚህ ወቅት ተጠቂው ሰው በድንገት ራሱን ይስታል፡፡ ይወድቃል፡፡ ታዲያ በዚህ ጊዜ የደም የስኳር መጠኑን ከፍ ለማድረግ ስኳር ቢሰጡት ወይም በጥብጠው ቢያጡት መልካም ነው፡፡ ከዚያም ቶሎ በአስቸኳይ ወደ ሆስፒታል መውሰድ አስፈላጊ ቀጣይ እርምጃ ነው፡፡ ከዚህ በተረፈ የስኳር ህመምተኞች በሌላ ጊዜ በህክምና ላይ እያሉ ጣፋጭ ነገሮች መውሰድ የለባቸውም፡፡ ምክንያቱም የህክምናው አላማ የበዛውን የደም የስኳር መጠን መቀነስ ነውና፡፡ ጣፋጭ ምግቦች ደግሞ የደም ስኳር መጠንን በኃይለኛ የመጨመር ባህሪ አላቸውና ነው፡፡ ስለዚህ ስኳር ነክ ምግቦች ላይ ጥንቃቄ ማድረጉ የተሻለ ነው፡፡ መልካም ጤንነት እንመኝልሃለን፡፡

Sport:ኢትዮጵያ ከወር በኃላ የሚጀመረውን የሴካፋ ዋንጫ ማዘጋጀት እንደማትችል በመጨረሻ ሰአት አሳወቀች

$
0
0

* ሴካፋ በኢትዮጵያ ውሳኔ ክፉኛ አዝኗል!

ኢትዮኪክ እንደዘገበው:-

የምስራቅ እና መካከለኛው የአፍሪካ አገራት የሚሳተፉበት የሴካፋ ውድድር ከአንድ ወር በኃላ November 24 – December 10 በኢትዮጵያ አዘጋጅነት ይካሄዳል ቢባልም ኢትዮጵያ ውድድሩን ማዘጋጀት እንደማትችል ለሴካፋ በመጨረሻ ሰአት አሳወቀች።
የምስራቅ እና መካከለኛው የአፍሪካ የእግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የሚዲያ ኃላፊ ሮጀር ሙሊንዳዋ ዛሬ እንዳስታወቁት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ውድድሩን ማዘጋጀት እንደማችይል የውድድሩ ቀናት በተቃረበበት ሰአት ማሳወቁ መደንገጣቸውን እና ብሎም ክፉኛ ማዘናቸውን ገልፀው፤ ውድድሩን ሱዳን አልያም ታንዛንያ ማዘጋጀት የሚችሉበትን አፋጣኝ ውስኔ እንደሚወስዱ አስታውቀዋል።
africa_2005-6_1128986520_addis-soccer3
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያልጠበቀ እና ድንገተኛ ውሳኔ ምክንያቱ በይፋ ባይገለፅም ፌዴሬሽኑ የገንዘብ ችግር እንደምክንያት ተቀምጧል። ኢትዮ ኪክ ጉዳዮን ለማጣራት ጥረት በዳረገበት መረጃ ምንም እንኳን ውድድሩ የምስራቅ አፍሪካ አገራት ቢሆን በፌዴሬሽኑ አካባቢ በምህራብ አፍሪካ የተከሰተው የኢቦላ ቫይረስ ለውድድሩ አማካይነት ከተለያየ የአፍሪካ አገራት በሚመጡ እንግዶች ላይ የመከሰት ስጋት ሊፈጠር ይችላል በሚል እንደሆነም ተሰምቷል።

ኢትዮጵያ ቀድም ባሉት ጊዚያት ውድድሩን ስፖንሰር ባደረጉት ሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲን ስያሜ ተሰጥቶት ማዘጋጀቷ ይታወሳል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከወራቶች በፊት ለማዘጋጀት እድሉን ተቀብሎ ውድድሩ ሊጀመር አንድ ወር ሲቀረው ወገቤን ከማለቱ ይልቅ በትክክል የገንዘብ ችግር እና የማዘጋጀት አቅሙ ከሌለው ፌዴሬሽኑ ቀደም ብሎ ለሴካፋ ማሳወቅ ይጠበቅበት ነበር።

በ2013 የሴካፋ ውድድር በኬንያ ሲዘጋጅ
ጎ ቲቪ 11.25 ሚልዮን የኬንያ ሽልንግ ከፍሎ ውድድሩን ስፖንዘር አድርጎታል።
የዘንድሮ ውድድር አዘጋጅ አገር ከተገኘ በውድድሩ ኬንያ፣ታንዛኒያ፣ቡሩንዲ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኢትዮጵያ፣ ጂቡቲ፣ሶማሊያ እና ኤርትራ ተሳታፊ ይሆናሉ።

Sport: የቱሬ እንቆቅልሽ: እውን የሲቲ አማካይ ክፍል ችግር አይቮሪኮስታዊው ነው?

$
0
0

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የያያ ቱሬ ጎሎች ለማንቸስተር ሲቲ ድል ወሳኝ እየሆኑ መጥተዋል፡፡ ሲቲ በእንግሊዝ እግርኳስ ከአናት እንዲቀመጡ የእርሱ አስተዋፅኦ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ችግሩ በማጥቃት እንቅስቃሴው ላይ የሚያሳርፈው በጎ ተፅዕኖ እየጎላ በሄደ ቁጥር የመከላከል ድክመቱ መጋለጡ ነው፡፡ በመሆኑም ያያ ቱሬ በሲቲ በሚኖረው ቆይታ ላይ ጥያቄዎች መነሳት ጀምረዋል፡፡
yaya toure
በእርግጥ በ28 ሚሊዮን ፓውንድ ክፍያ ባርሴሎናን ለቅቆ ማንቸስተር ሲቲን ሲቀላቀል ቱሬ ዛሬ ለደረሰበት ደረጃ ይበቃል ብሎ የጠረጠረ አልነበረም፡፡ ሮቢንሆ በኢቲሃድ ያልተሳካ ጊዜን ካሳለፈ በኋላ ሲቲ ብቃታቸውን አሟጠው የጨረሱ ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋይ ተጨዋቾች ማረፊያ እንዳይሆን ተሰግቶ ነበር፡፡ ቱሬ ግን ለእንግሊዝ እግርኳስ የተሰራ ሰው ነው፡፡
ምንም እንኳን በወቅቱ በጋርዲዮላ ባርሴሎና ውስጥ በቋሚነት የመጫወት ዕድሉ ያልነበረው ቢሆንም ለፕሪሚየር ሊጉ እግርኳስ ፍፁም ተስማሚ የሆነ ተጨዋች ነበር፡፡ ቅልጥፍናው እና ጥንካሬው በሊጉ ለመጫወት ብቁ አድርገውታል፡፡ የእንግሊዝ እግርኳስ የተጋጋለ ባህሪይ ያንን መቋቋም የሚችሉ ተጨዋቾችን መያዝ ግድ ይላል፡፡ በተለይ በአማካሪ ክፍል ያንን ማድረግ ወሳኝ ነው፡፡

ግዝፈት እና ቅልጥፍና በአማካይ ክፍል ያለው አስፈላጊነት

ቱሬ የአርሴናል ጥንካሬ መሰረት ከነበሩ እንደ ፓትሪክ ቪዬራ፣ ጂልቤርቶ ሲልቫ እና ኢማኑኤል ፐቲ ጋር ይመሳሰላል፡፡ ሞውሪንሆ ከ2004/2007 በቼልሲ በነበሩበት ወቅት በቡድናቸው ከያዟቸው ተጨዋቾች ጋር ይቀራረባል፡፡ ፕሪሚየር ሊጉን ካደመቁ ምሉዕ አማካዮች ሁሉ ቀዳሚው እንደሆነ ከሚነገርለት ማይክል ኤሲዬን (ቪዬራ እና ሮይ ኪን ለክብሩ ሊፎካከሩ ይችላሉ) ጋር ማወዳደርም ይቻላል፡፡

እግርኳስ ከአስር ዓመት በፊት ከነበረው ብዙም አልተለወጠም፡፡ በእርግጥ ቬንገር ግዙፍ እና ጉልበተኛ አማካዮችን ትተው ‹‹ደቃቃ›› አማካዮችን መጠቀም መርጠዋል፡፡ (ይህም በሊጉ ስኬታቸው ላይ ጉዳት አድርሷል)፡፡ ባርሴሎና እና ስፔን ጨዋታዎችን ግዙፍ ባልሆነ ቴክኒሺያኖች በበላይነት መቆጣጠር ሲጀምሩ የፈረንሳዊው አሰልጣኝ ውሳኔ ትክክል መሰለ፡፡ እውነታው ግን ግልፅ ነበር፡፡ ስኬታቸው የተመሰረተው በሆልዲንግ አማካዩ ጥንካሬ ላይ ነው፡፡ ያንን ሚና የሚወጣው ኤድሚልሰን፣ ያያቱሬ፣ ማርኮስ ሴና አልያም የዓለማችን ምር ሆልዲንግ አማካይ ሰርጂዮ ዙስኬትስ ሊሆን ይችላል፡፡ ስኬታማ ለመሆን ጨዋታዎችን በበላይነት የሚቆጣጠር የተከላካይ አማካይ ማስፈለጉ ግን አያጠራጥርም፡፡ የተከላካይ መስመሩን ያግዛል፡፡ በማጥቃ እንቅስቃሴ ላይ የሚሳተፉ ተጨዋቾች በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ መደላደሉን ያመቻቻል፡፡

ይህ እውነታ በአብዛኛው ሰው ዘንድ ከታወቀ ከ10 ዓመት በላይ ይሆነዋል፡፡ ዲዲዬ ዴቮ እና ክሎድ ማኬሌሌ የዚህ ሚና መገለጫዎች ነበሩ፡፡ እንደ እነ ኤሲዬን፣ ቪዬራ፣ እና ዳ ቪድሰን የመሳሰሉ ‹‹ምሉዕ›› ተጨዋቾች ሚናውን ይበልጥ አሻሻሉት፡፡ በቅርቡ ሽዌንስታይገር እና አርቱሮ ቪዳል በሚናው ደምቀው ታይተዋል፡፡ ሌሎች እንደ አንድሬያ ፒርሎ፣ ቬሮን፣ ማይክል ካሪክ እና ዣቢ አሎንሶን የመሳሰሉ ተጨዋቾች በበኩላቸው ባፈገፈገ ሚና ልቀው ታይተዋል፡፡ ይህ የሆነው ከጎናቸው የሚሰለፈው የተጋጣሚ ቡድንን እንቅስቃሴ በመግታት ላይ የሚያተኩረው የተከላካይ አማካይ (destroyer) ለመፍጠር የሚያስፈልጋቸውን ጊዜ እና ቦታ እንዳያገኙ ለማስቻል ያለመታከት ስለሚለፉ ነው፡፡

በትልቅ ደረጃ ላይ በሚከናወኑ ጨዋታዎች በአማካይ ክፍል ግዙፍ እና የማይዳከሙ ተጨዋቾችን መያዝ የግድ እየሆነ መጥቷል፡፡ በፕሪሚየር ሊጉ ወሳኝ የሆነውን ያህል በአውሮፓም አስፈላጊ ነው፡፡ ያያ ቱሬ የበላይነቱ እና ታታሪነቱ ጎልቶ በሚወጣበት ሊግ ስኬታማ መሆን ችሏል፡፡ አይቮሪኮስታዊው የሲቲ ‹‹ቁልፍ ሰው›› በመሆኑ ከተጣለበት ኃላፊነት እጅጉን ተጠቅሟል፡፡ ቡድኑን እንዲቆጣጠር ተፈቅዶለታል፡፡

ሁሉም የቡድኑ እንቅስቃሴ የሚያልፈው በእርሱ በኩል ነበር፡፡ በአጭሩ መሪ ነበር፡፡ በባርሳ የቡድኑ አንድ አካል ብቻ ነበር፡፡ በሲቲ ግን እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት የተሻለ ተጨዋች ሆነ፡፡ ተፅዕኖውም እየጎላ ሄደ፡፡ በባርሳ ሳለ ከሶስቱ አማካዮች አንዱ ነበር፡፡ በሲቲ ግን ወደፊት እየሄደ በተጋጣሚ ቡድን ላይ አደጋ እንዲጥል ፈቃድ ተሰጠው፡፡ ሚናውን በአግባቡ መወጣት እንደሚችልም አስመሰከረ፡፡ ጨዋታዎች ከባድ ሲሆኑ አልያም የማሸነፊያውን ጎል ማስቆጠር አስቸጋሪ ሲሆን እርሱን እንደ አጥቂ መጠቀምም እየተለመደ መጣ፡፡ የማንቺኒ የመጫወቻ ካርድ ቱሬን ወደፊት ተጠግቶ እንዲጫወት ማድረግ ነበር፡፡ ውጤቱም ያማረ ነበር፡፡ የውሳኔውን ፍሬያማነት የተመለከቱት ማኑኤል ፔሌግሪኒም ወደፊት እየሄደ የማጥቃቱን ሂደት እንዲያግዝ የበለጠ ነፃነት ሰጡተ፡፡ ቱሬ ያለ ስጋት ወደፊት እንዲሄድ እና የተከላካይ መስመሩን ከአደጋ ለመከላከል በማሰብ ቺሊያዊው አሰልጣኝ ፈርናንዲንሆን ወደ ቡድኑ ቀላቀሉ፡፡ ፔሌግሪኒ በሲቲ በቆዩበት የመጀመሪያው የውድድር ዘመን ቱሬ 20 ጎሎችን በስሙ አስመዘገበ፡፡ ለሲቲ የፕሪሚየር ሊግ ስኬት ቁልፉ ሚና ከተጫወቱት ተጨዋቾችም ግንባር ቀደም ሆነ፡፡
ሆኖም በአሁኑ ወቅት የቱሬ የሲቲ ቆይታ ወደ ማብቂያው ተቃርቦ ይሆን? በቡድኑ ውስጥ እንቅፋት እየሆነ መጥቷል ለማለት የሚያስችል አሳማኝ ምክንያት ይኖር ይሆን? ቱሬን በአማካይ ክፍሉ የያዘው ሲቲ በአውሮፓ ውጤታማ መሆን ይችላል?

የአማካይ ክፍል እንቅፋት?

ቱሬ በአማካይ ክፍል የሚፈጠረው ችግር በጉልህ መታየት የጀመረው ባለፈው የውድድር ዘመን ነው፡፡ ከዚያ በፊት ሲ በአውሮፓ መድረክ በአማካይ ክፍል የበላይነት ሲወሰድበት እንደ ምክንያት የሚጠቀሱት የቡድኑ ትስስር ማጣት ሮቤርቶ ማንቺኒ የሚመርጡት ታክቲክ እና የመሳሰሉት ነገሮች ነበሩ፡፡ የተጠቀሱት ምክንያቶች እውነት እና ፍትሃዊ ናቸው፡፡ አንድ ቡድን በአውሮር መድረክ ስኬታማ ለመሆን 100 ፐርሰንት ቁርጠኝነት ሊኖረው ይገባል፡፡ ህብረቱ የማያወላዳ መሆን አለበት፡፡ በተለይ ኳስ በተቃራኒ ቡድን ተጨዋቾች እግር ስር ስትሆን የተጨዋቾች ትጎት ወሳኝ ነው፡፡ በጥረ ሁኔታ የሚከላከሉ ቡድኖች ቻምፒዮንስ ሊግን የሚያሸንፉት በአጋጣሚ አይደለም፡፡ ዋንጫዎችን የሚያስገኘው መከላከል ነው፡፡ ሲቲን በአውሮፓ መድረክ ስናየው የምንመለከተው ቱሬ በመከላከሉ ያለበትን ድክመት ነው፡፡

ባለፈው የውድድር ዘመን በቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ ሲቲ በሜዳው በባየርን ሙኒክ 3-2 ሲሸነፍ የሲቲ የአማካይ ክፍል ግራ ተጋብቶ አምሽቷል፡፡ የጀርመኑ ቡድን ተጨዋቾች የሚያደርጓቸውን ፈጣን የኳስ ቅብብሎች መቆጣጠር ተስኖት ታይቷል፡፡ የሲቲ አማካይ ክፍል ደካማ እና ተጋላጭ ነበር፡፡ ቱሬ ተጫዋቾችን ተጠግቶ መጫወት አልቻለም፡፡ ቀርፋፋ መስሎም ታይቷል፡፡ በድካም የዛለ ሰው ይመስል ነበር፡፡ ‹‹በዓለም እግርኳስ እጅግ የተሟላ ተጨዋች›› ተደርጎ የሚቆጠረውን አማካይ አይመስልም ነበር፡፡ ምናልባት ጨዋታው የተደረገው ከአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊው ክለብ ጋር መሆኑ ችግሩን አጉልቶት ይሆናል፡፡ ነገር ግን ችግሩ በሌሎች ጨዋታዎች ላይም ተስተውሏል፡፡

ይህ ችግር በሊጉም መታየት ጀምሯል፡፡ ሲቲ ከሜዳው ውጪ ከስዋንሲ ጋር ባደረገው ጨዋታ ላይ ቱሬ ወደ ኋላ ተመልሶ የመከላከል ፍላጎት አጥቶ ታይቷል፡፡ ሲቲ ከሜዳው ውጪ ከቶተንሃም ጋር ያደረገውን ጨዋታ የተመለከተው ጋሪ ኔቭል ለፈርናንዲንሆ የሚሆን የአድናቆት ቃል ለማግኘት ብዙ ጥሯል፡፡ ብቻውን የአማካይ ክፍሉን የተከላከለበት መንገድ ለማመን የሚያስቸግር ነበር፡፡ ቱሬ ሲቲን በመከላከሉ ረገድ ሊያግዝ አለመቻሉ ትችቶች ጎልተው እንዲሰሙ አድርጓል፡፡
20 ጎሎች የተጫዋችን ድክመት ሊሸፍኑ ይችላሉ፡፡ ወደፊት እየሄደ እንዲያጠቃ የበለጠ ፈቃድ እንደተሰጠው ግልፅ ነው፡፡ ሆኖም ሲቲ በፈጣሪ ተጫዋቾች እና በታላላቅ አጥቂዎች የታደለ ነው፡፡ በአውሮፓ መድረክ ውጤታማ ለመሆን ቁልፉ ጨዋታዎችን በተሳካ መንገድ መቆጣጠር መቻል ነው፡፡ ሲቲ በአውሮፓ መድረክ ባደረጋቸው የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎች ተራ ቡድን መስሎ ታይቷል፡፡ ለመልሶ ማጥቃት በቀላሉ ይጋለጥ ነበረ፡፡ ተጋጣሚዎች በርካታ አጋጣሚዎችን እንዲፈጥሩም ይፈቅድ ነበር፡፡ በእርግጥ ያስተናገደው ሁለት ጎሎችን ብቻ ነው፡፡ ያም ቢሆን በሚያሳቅቅ መል ክፍት ነበር፡፡ ቡድ ፈርናንዶን በማጣቱ እጅጉን ተጎድቷል፡፡ በዚያ ላይ ቱሬ በመሀል ሜዳ ያለበትን ችግር አጋልጧል፡፡ በዚያ ላይ ቴሬ በመሀል ሜዳ ያለበትን ችግር አጋልጧል፡፡ ፈርናንዶ የተገዛው ፈርናንዲንሆን እንዲያግዝ ነው፡፡ እርሱ ባልነበረባቸው ጨዋታዎች አማካይ ክፍሉ ደክሞ ታይቷል፡፡ ከአስቶን ቪላ ጋር በተደረገው ጨዋታ ላይ የእርሱ ወደ ሜዳ መግባት ጨዋታውን ለውጦታል፡፡ አማካይ ክፍሉ እንዲረጋጋ አድርጓል፡፡ ሲቲም መልሶ ጨዋታውን መቆጣጠር ችሏል፡፡ ፈርናንዲንሆን ከወጣ በኋላ የሲቲ የአማካይ ክፍል በቱሬ እና ፍራንክ ላምፓርድ ተዋቀረ፡፡ በዚያን ወቅት ቪላ ጥቃት በሰነዘረባቸው አጋጣሚዎች ሁሉ አስፈሪ ነበር፡፡

የአማካይ ክፍሉ ከስንት ተጨዋቾች ይዋቀር

ፈርናንዲንሆ ፈርናንዶ በአንድነት ሲሰለፉ ሲቲ ጠንካራ እና የበለጠ ዲሲፕሊን ያለው ቡድን ይሆናል፡፡ ያም ቢሆን በአውሮፓ ውጤታማ ለመሆን የአማካይ ክፍልን በሶስት ተጨዋቾች መገንባት ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ምክንያት ፔሌግሪኒ ሊወቀሱ ይችላሉ፡፡ የደቡብ አሜሪካውያንን 4-2-2-2 ፎርሜሽን መጠቀማቸው የሲቲን አማካይ ክፍል ተጋላጭ ያደርገዋል፡፡ ቴሬን በተደራቢ አጥቂነት ቢያሰልፉት እንኳን ሲስቁም ወደ 4-2-3-1 አልያም 4-3-3 የመቀየር ዕድሉ የጠበበ ነው፡፡

ቱሬ እንደ ሶስተኛ ሰው ድጋፍ መስጠት አልቻለም፡፡ ሚሱት ኦዚል፣ ሁዋን ማታ እና ዌስሊ ሽናይደርን እንደመሳሰሉ ተጨዋቾች ቡድኑን በመከላከሉ ረገድ አያግዝም፡፡ ሆኖም ጨዋታውን ለመቆጣጠር እና በበላይነት ለመምራት በጋራ ጥረት ማድረግ ወሳኝ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ሎካሞድሪች፣ ማሪዮ ጎትዘ፣ አንሄል ዲ ማሪያ፣ ኦስካር እና ፋብሪጋዝን የመሳሰሉ ዘመናዊ 10 ቁጥር ተጨዋቾች ግን ለቡድናቸው የበለጠ የመከላከል ሽፋን ይሰጣሉ፡፡ ይህም ቡድኑ በመከላከሉ ጥብቅ እና አስተማማኝ እንዲሆን ያደርጋል፡፡ የቼልሲን የአማካይ ክፍል አማራጮች ተመልከቱ፡፡ ኔማኒያ ማቲች፣ ራሚሬዝ፣ ኦስካር እና ፋብሪጋዝን ታገኛላችሁ፡፡ የምትመለከቱት አስደናቂ የማጥቃት ኃይል ብቻ አይደለም፡፡ መከላከል ላይ ጠንካራ ናቸው፡፡

የሲቲ መፍትሄ ምን ይሆን? ቱሬ በሜዳ ውስጥም ሆነ ከሜዳ ውጪ ችግር ፈጣሪ ሆኗል፡፡ ወኪሉ ተጨዋቹ ደስተኛ አለመሆኑን መናገሩ በቡድኑ ውስጥ የነበረውን ህብረት አናግቷል፡፡ አይቮሪኮስታዊው ለበርካታ ዓመታት የሲቲ ቁልፍ ተጨዋች እንደነበር አይካድም፡፡ ሲጎርፉለት የከረሙ ውዳሴዎች በባህሪው ላይ ተፅዕኖ ሊፈጥሩ እንደሚችሉ መጠርጠር መልካም ነው፡፡ ትኩረት ማጣት እና ለራስ በሚሰጥ የተጋነነ ግምት ምክንያት የሚፈጠር እብሪት ሊከሰት እንደሚችል መረዳት አዋቂነት ነው፡፡ ቱሬ ማረጋገጥ ያለበት ምንም ነገር እንደሌለ ይሰማው ጀምሯል፡፡ አሳሳቢው ነገር ይህ ነው፡፡ እንደዚያም ሆኖ ከመጀመሪያ አሰላለፍ ውጪ አይሆንም፡፡

የትኛውም ተጨዋች ከክለብ በላይ ሊሆን አይችልም፡፡ አንድ ተጨዋች የብቃቱን 100 በመቶ አውጥቶ ቡድኑን እያገለገለ እንዳልሆነ እና የቡድኑን ሚዛን ለማናጋት እየተንደረደረ መሆኑ ከታወቀ ቡድኑ ፊቱን ወደ ሌላ አማራጭ ማዞር ይጠበቅበታል፡፡ ታዲያ ሲቲ ሊያማትር የሚገባው ወዴት የሆነ? ጀምስ ሚልነር ትክክለኛ ምትኩ ይመስላል፡፡ ሚልነር ለሲቲ ከሶስት ተጨዋቾች የተዋቀረ የአማካይ ክፍል ሊያስገኝ ይችላል፡፡ ለቦታው የሚያስፈልገውን የታክቲክ ዲሲፕሊን እና ታታሪነት ያሟላል፡፡ ለዚህ እንደ ማሳያ የሚያገለግለው አንሄል ዲ ማሪያ ባለፈው የውድድር ዘመን በመሀል ሜዳ የተፈጠረው ተፅዕኖ ነው፡፡

ሲቲ ሚሊነርን የአማካይ ክፍሉ ቁልፍ ተጨዋች ቢያደርገው ተጠቃሚ ይሆናል፡፡ ከሚቀጥለው የውድድር ዘመን ጀምሮ ከቱሬ ይልቅ ለእርሱ ቅድሚያ ቢሰጥ እርምጃው ብልህነት ይሆናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ክሮስ ባርክሌይ ጋር የተያያዙት ጭምጭምታዎች ትርጉም ይሰጣሉ፡፡ ታዳጊው እጅግ ‹‹ምሉዕ›› ከሆነ ተስፈኛ እንግሊዛውያን እግርኳስ ተጨዋቾች ቀዳሚው ነው፡፡ከጉዳት ነፃ መሆን ከቻለ የዓለም ምርጡ ተጨዋቾች የመሆን ዕድል አለው፡፡

ሲቲን ወደ እንግሊዝ እግርኳስ አናት በመምራት ሂደት የቱሬ ሚና ወሳኝ ነበር፡፡ ከአውሮፓ ትላልቅ ተጨዋቾች አንዱ ሊሆን ችሏል፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት የቀድሞው ብቃቱ አብሮት የለም፡፡ የወንድሙ ሞት እና በክረምቱ ያከናወነው የዓለም ዋንጫ ትኩረቱን እና ጉልበቱን አሳጥቶታል፡፡ የማሸነፍ ረሃቡ ተቀዛቅዞም ይሆናል፡፡ ምክንያቱ ምንም ቢሆን ሲቲ ያለ ቱሬ ለመጓዝ መዘጋጀት አለበት፡፡ በአውሮፓ መድረክ ስኬታማ ለመሆን የነደፈውን ውጥን ወደፊት ማራመድ የሚችለው ያንን ሲያደርግ ብቻ ነው፡፡

Breaking News: አብርሃ ደስታ; ሀብታሙ አያሌው; የሽዋስ አሰፋ ; ዳንኤል ሺበሺ በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው

$
0
0

Habtamu abrhayeshiwas daniel
• አብርሃ ደስታ የሁለት ድርጅቶች አባል ነው የሚል ክስ ተመስርቶበታል

• ወደ አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ ታዟል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በልደታ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ምድብ ወንጀል ችሎት ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ በተሰየመው ችሎት 10 ተከሳሾች በፌደራል አቃቢ ህግ በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከ100 ገጽ በላይ የክስ ቻርጅ የተነበበላቸው ሲሆን ከክስ ቻርጁ ጋር ከ300 ገጽ በላይ የምርመራ ሰነድ ቀርቦባቸዋል፡፡

የክሱ መዝገብ የተከፈተው ዘላለም ወርቃገኘሁ በተባለውና ‹‹የግንቦት 7 አመራር ነው፡፡›› ተብሎ ክስ በተመሰረተበት ግለሰብ ሲሆን በዚህ የክስ መዝገብ የተካተቱትም፡-

1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ
2ኛ ተከሳሽ ሀብታሙ አያሌው
3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ
4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ
5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ
6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ
7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን
8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ
9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ
10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው

ለሁሉም ተከሳሾች ከዛሬ በፊት ክስ እንዳልደረሳቸውና ዛሬ ፍርድ ቤት ውስጥ እንደተሰጣቸው ታውቋል፡፡ በችሎቱ 6ኛ ተከሳሽ ከሆነው ዮናታን ወልዴ በስተቀር ሁሉም ያለ ጠበቃ የቀረቡ ሲሆን ጠበቃዎቹ ያልቀረቡበት ምክንያትም ጠበቆቹ ደምበኞቻቸው የሚቀርቡበት ቦታና ጊዜ ስላልተነገራቸው እንዲሁም ቀደም ብለው እንዳይገናኙ በመደረጋቸው መሆኑን አቶ ኃብታሙ አያሌው ችሎቱ ላይ ተናግሯል፡፡

ከሳሹ የፌደራል አቃቢ ህግ በ1996 የወጣው የወንጀል ህግ እና የጸረ ሽብር ህግ ጠቅሶ ክስ ያቀረበ ሲሆን ክሶቹ በሁለት ዋና ዋና ጭብጦች ቀርበዋል፡፡ የመጀመሪያው ጭብጥ ‹‹ከሽብርተኛ ቡድኖች ጋር በጋራ በመስራት›› የሚል ሲሆን ‹‹ህገ መንግስቱንና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ፣ የመንግስትን መሰረተ ልማት በማፈራረስ፣ ህዝብን ለአመጸ በማነሳሳት መንግስትን መለወጥ አላማው አድርጎ ከሚሰራውና ራሱን ግንቦት 7 ብሎ ከሚጠራው ቡድን ጋር አባል በመሆንና በወንጀል ድርጊቶች በመሳተፍ›› በሚል ቀርቧል፡፡

ሁለተኛው የክስ ጭብጥ ‹‹የሽብር ቡድን አመራር በመሆን›› የሚል ሲሆን በተለይም የአንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ‹‹የሽብር ቡድኑ አመራር በመሆንና አባል በመመልመል›› በሚል የክስ ጭብጥ ቀርቦበታልል፡፡

ከ2-5ኛ የክስ መዝገብ የሚገኙት ማለትም ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሽ፣ አብርሃ ደስታና የሸዋስ አሰፋ ‹‹ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲን ከለላ በማድረግ ግንቦት 7 የተባለውን የሽብር ቡድን አላማ ለማሳካት ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ፋሲል የኔ ዓለምና ሌሎች የሽብር ቡድኑ አባላት ጋር በስልክ በመነጋገርና በማህበራዊ ድህረ ገጸ የተለያዩ መልዕክቶችን ተለዋውጠዋል›› የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ አብርሃ ደስታ ከግንቦት 7 በተጨማሪ ‹‹ደምኢት የተባለ ቡድን አባል ነው፡፡›› የሚል ክስ ቀርቦበታል፡፡

በስተመጨረሻም ፍርድ ቤቱ ሁለት ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ አንደኛው ረቡዕ ጥቅምት 26/2007 ዓ.ም 3 ሰዓት ተከሳሾቹ ዋስትና ይሰጣቸው አይሰጣቸው በሚለው ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤቱ ከተከሳሾቹ ጠበቆች ጋር ተማክሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሏል፡፡ በሁለተኛነት ተጠርጣሪዎቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ቀደም ሲል ለአራት ወራት ወደቆዩበት ማዕከላዊ እስር ቤት እንዳይመለሱ ፍርድ ቤቱን ስለጠየቁ ፍርድ ቤቱ በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት (3ኛ) እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

ተከሳሾቹ ትናንት ጥቅምት 20/2007 ዓ.ም አራዳ ምድብ ችሎት ይቀርባሉ ተብሎ የነበር ቢሆንም ሳይቀርቡ ቀርተዋል፡፡ በተመሳሳይ ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ጠዋት ወደ ልደታ ፍርድ ቤት ተወስደው የነበረ ቢሆንም እንደገና ወደማዕከላዊ ተመልሰው ከሰዓት እንዲቀርቡ ተደርገዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ኾኑ

$
0
0

ሐራ ዘተዋሕዶ

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ፤ የከምባታ ሐዲያ ጉራጌና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ የበላይ ሓላፊ

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ፤ የከምባታ ሐዲያ ጉራጌና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ የበላይ ሓላፊ

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ፤ የከምባታ ሐዲያ ጉራጌና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬ፣ ጥቅምት ፳፩ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. ዐሥረኛ ቀን የቀትር በፊት ውሎው ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ኾነው እንዲሠሩ መደበ፡፡

ብፁዕነታቸው፣ ትላንት በተጠናቀቀው የሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያ፣ የፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት ኾኖ በተደነገገው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ኾነው እንዲሠሩ በምልአተ ጉባኤው የተመደቡት በርእሰ መንበሩ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከተጠቆሙ በኋላ ነው፡፡

ምደባው አስመራጭ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሦስት ዕጩዎች ከተለዩ በኋላ በዕጣ እንዲከናወን ታስቦ እንደነበር ተገልጧል፡፡ ይኹንና በፓትርያርኩ ጥቆማ እንዲወሰን የተደረገው፣ የመንበረ ፓትርያርኩ መቀመጫ የኾነው አዲስ አበባ የፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት በመኾኑ ጥቆማውም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ እንዲሰጥ ምልአተ ጉባኤው ከተስማማበት በኋላ ነው፡፡

ቢራቢሮ … (ከሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 31.10.2014 (ሲዊዘርላንድ –  ዙሪክ)

 

ነይ እሰኪ ዘንድሮ

አለፈልግም ከርሞ

የለኝም አርምሞ

              ሁለመናዬ አሮ

              በበቀል ተነክሮ

             ቀለም የለሽ ኑሮ፣

             መስቃ ተዘርዝሮ

             መብቴ ተዘሮ

             ሁኛለሁ ደንቆሮ።

አንቺ ቢራቢሮ

ሕይወት ቢራቢሮ

ኑሮ ቢራቢሮ

ነፍሴ ቢራቢሮ

ተስፋ ቢራቢሮ

አትሁኝ በረሮ

አታፍቅሪ ጦሮ።

              ነጠብጣቤ አሮ

              ዓይኔም ተማርሮ

              በበላኃሰቦች እንዲህ ተወሮ

              ከምሾ ተድሮ

              ከዋይታ ተዳብሎ።

አንቺ ቢራቢሮ

ሕይወት ቢራቢሮ

ኑሮ ቢራቢሮ

ነፍሴ ቢራቢሮ

ተስፋ ቢራቢሮ

አትሁኝ በረሮ

አታፍቅሪ ጦሮ።

              ገሳ ተንተርሶ

              ሞረሽን ተንፍሶ

              በደልን ተቋድሶ፣

              ዛሬ ተቀልብሶ

              እህህን ተለብሶ።

አንቺ ቢራቢሮ

ሕይወት ቢራቢሮ

ኑሮ ቢራቢሮ

ነፍሴ ቢራቢሮ

ተስፋ ቢራቢሮ

አትሁኝ በረሮ

አታፍቅሪ ጦሮ

              ፍሬ ዘሬ ሁሉ …

              …. በምጣድ ታምሶ

              አመድ ተነስንሶ

             ትብያ ተበስብሶ

             ድንጋዩን ቀልብሶ፣

              ተቀበረ ምሶ

              ም ሶ።

አንቺ ቢራቢሮ

ሕይወት ቢራቢሮ

ኑሮ ቢራቢሮ

ነፍሴ ቢራቢሮ        ቢራቢሮ …

ተስፋ ቢራ ቢሮ

አትሁኝ በረሮ

አታፍቅሪ ጦሮ።

             ርም ተበጥሶ

             ማት ተጠናብሶ

             ትብ ቢሆን ጢሶ፣

             ዳ ተሰልሶ

             ብር … አሳር ትቢያ ተላብሶ።

አንቺ ቢራቢሮ

ሕይወት ቢራቢሮ

ኑሮ ቢራቢሮ

ነፍሴ ቢራቢሮ

ተስፋ ቢራቢሮ

አትሁኝ በረሮ

አታፍቅሪ ጦሮ።

             ሥርዓት ተጥሶ

             ፍትህ ተገርስሶ

             ንጋፍ ተኮፍ

             ኩም ተፈውሶ፣

             ዙኀኑ አንሶ

             መጠጊያ ተው

አንቺ ቢራቢሮ

ሕይወት ቢራቢሮ

ኑሮ ቢራቢሮ

ነፍሴ ቢራቢሮ

ተስፋ ቢራቢሮ

አትሁኝ በረሮ

አታፍቅሪ ጦሮ።

              ስልቻ ቃልቻ

              ብልቻ ጉልቻ

              አንተ አለህ መፍቻ፣

              ድሕን አንተው ብቻ

              ሰልችቶናል ግቻ

የ እ ን ጉ ቻ ች ር~~~~~ ዛ

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

                  ጥቅምት 11 ቀን 2001 . ዙሪክ አውሮፕላን ማረፊያ –  ሲዊዘርላንድ

Comment

በልብ በሽታ የሚሰቃዩት አቶ በረከት ስሞኦን ለዳግም ህክምና ሳውዲ አረቢያ ሾልከው ገቡ

$
0
0

ኢትዮጵያን ሃገሬ ጅድ በዋዲ ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው

በልብ በሽታ የሚሰቃዩት አቶ በረከት ስሞን ህመሙ ጠንቶባቸው ከሁለት ወር በፊት በሼክ አላሙዲን የግል አውሮፕልና ተጭነው በድበቅ ለህክመና ሳውዲ አረቢያ መግባታቸው ይታወሳል። በወቅቱ ሳውዲ አረቢያ ጅዳ የሚገኝ አንድ «ቡግሻን» hospital እየተባለ የሚጠራ ሪፈራል ሆስፒታል የልብ ቧንቧ ማስፋት ህክምና ቢደረግላቸውም የባለስልጣኑ የጤነነት ሁኔታ የሚጠበቀውን ያህል ለወጥ ባለማሳየቱ ለዳገም ህክምና ቀጠሮ ተሰቷቸው ከሳምታት ቆይታ በሃላ ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን መዘገባችን ይታወሳል ።
Bereket Simon weeping with his wife over Meles Zenawi's death
ይህ በዚህ እንዳለ ዛሬም የአቶ በረከት ጤንነት መልካም ሁኔታ ላይ እንዳልሆነ ምንጮች የሆስፒታሉን የምርመራ ውጤት አብነት ጠቅሰው ይናገራሉ ። አቶ በረከት በጤነታቸው መታወክ ፍጹም መረጋጋት እንደማይታይባቸው የሚገልጹት እንዚህ ውስጥ አዋቂዎች ቀደም ሲል ባለስልጣኑ ህክምና ላይ በነበሩበት ወቅት ወደ ሳውዲ አረቢያ በሚስጠር ለህክምና መግባታቸውን ተከትሎ በተለያዩ ድህረገጾች ዜናው በስፍት መናፈሱ በውስጣቸው በተፈጠረው አለመረጋጋት በልባቸው ምት አለመስተካከል በወቅቱ በቂ ህክማና መውሰድ እናዳልቻሉ ታውቋል። የአቶ በረከት የጤነንት ሁኒታ ዛሬም አስተማማኝ እንዳልሆነ የሚያውሱ እንዚህ የአይን እማኞች ከእለት ተዕለት የባለስልጣኑ የአካል መጠን በማይጠበቅ ሁኔታ መቀነስ እና የፊታቸው ገጽታ መለዋወጥ በውስጣቸው መልካም ነገር እንደማይታይ ያሳብቃል ብለዋል።

የአቶ በረከት ስሞኦን ህይወት ለመታደግ የአቅማቸውን ያህል ጠረት እያደረጉ የሚገኙ «ቡግሻን» hospital የሳውዲ አረቢያ ሆስፒታል ዶክተሮች ሰለበሽታው አደገኝነት ግንዘቤ በማስጨበጥ አቶ በረከት ከተለያዩ መጠጦች እና አይምሮ አደዛዥ እጾች መራቅ እንዳለባቸው እና የጤነንታቸው ሁኔታ አስተማማኝ ሁኔታ ከሲደርስ እረፍት መስውሰድ እንደሚገባቸው ሙያዊ ምክሮቻቸውን ለገሰዋቸዋል። ይህ በዚህ እንዳለ አቶ በረከት ለህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ ሲያቀኑ የህክምና ውጪያቸውን እየሸፈኑ ከሚገኙት ሼክ አላሙዲን ባሻገር ለኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ባለስልጣናት ሚስጠር መሆኑ አያሌ ወገኖችን በስፋት እያነጋገር ነው ። ከሁለት ወር በፊት አቶ በረከት እኩለ ለሊት ከቦሌ አይሮፕላን ማረፊያ ወደ ሳውዲ አረቢያ በሼክ አላሙዲን የግል አይሮፕልና በድብቅ ለህክማን መግባታቸው ለኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ከፍተኛ ባለስልጣናት ወሬው የደረሰው እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዘ-ሃበሻ እና ጎልጉል ድህረገጾች በተለቅቁ መረጃዎች መሆኑን የሚናገሩ ምንጩች ለሁለተኛ ግዜ ዳግም ህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ ሲመለሱ በሼክ አልሙዲን በኩል በክበር «በፕሮቶኮል» ሊገቡ እንደሚቸል በወቅቱ ከጅዳ ቆንሳል ጽ/ቤት የወጡ መርጃዎች ቢያረጋግጡም የአቶ በረከት ስሞኦን እንደ ተለመደ በድብቅ ወደ ሳውዲ አረቢያ መግባት ባለስለስልጣኑ በውስጥም በውጨም ጥሩ ወዳጅ እንደሌላቸው የሚነገረውን ሃቅ ያጠናክረዋል ብለዋል ።
አቶ በረከት ትላንት በተደረገላቸው ምርመራ የቅርብ ክትትል እንደሚያሻቸው የሚገልጹ የሆስፒታል መረጃዎች ባለስልጣኑ የተሰጣቸውን ምክር እና የተለያዩ መደሃኒቶቻቸውን ይዘው ከሆስፒታሉ ውጭ ወደ ሚገኘው ምስጢራዊ ማረፊያቸው ማቃናታቸው ተገልጾል፡ ይህ በዚህ እንዳለ አሁን ዘግይቶ በደረሰን ዜና መስረት አቶ በረከት ስሞኦን ዛሬ ማምሻውን ለአስቸኳይ ጉዳይ ህክምናቸውን አቋርጠው ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱ ምስጢራዊ መረጃዎቻችን አክለው አረጋግጠዋል ።


ሰበር ዜና – ቅ/ሲኖዶስ: ማኅበረ ቅዱሳን እየተመራበት ባለው መተዳደርያ ደንቡ እስከ መጪው ግንቦት እየሠራ እንዲቆይ ወሰነ፤ የማኅበሩ መተዳደርያ ደንብ በአዲስ መልክ ተሻሽሎ ይዘጋጃል

$
0
0

mahibere-kidusan-logo

ሐራ ዘተዋሕዶ

  • የመተዳደርያ ደንቡን ማሻሻያ ረቂቅ ለግንቦቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አዘጋጅቶ የሚያቀርብ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ ኮሚቴ ተቋቁሟል፡፡
  • ማኅበሩ በጊዜአዊነት በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር ለመምሪያው የበላይ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ ተጠሪ ኾኖ አገልግሎቱን በመፈጸም ይቆያል፡፡
  • ጠቅላይ ቤቴ ክህነቱ ዘመናዊውን የኹለትዮሽ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ ሥርዐት መከተሉ ማኅበሩ ከፋይናንስ ሥርዐቱ ጋራ የሚጣጣሙ የሒሳብ ሰነዶችን ለመጠቀም ያስችለዋል፡፡
  • የኤጲስ ቆጶሳት ሢመት መመዘኛ ሕግ ጸደቀ፤ በመጪው ግንቦት የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት እንደሚፈጸም ተጠቁሟል

 

መንግስት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ገጥሞታል • ‹‹መንግስት የብርን ዋጋ በቅርቡ ‹ዲቫሊዌት› ሊያደርግ ይችላል››

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ እንደዘገበው፦

የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደገጠመው የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ አንድ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የብሄራዊ ባንክ ከፍተኛ የኢኮኖሚ አጥኚ እጥረቱ መኖሩን አረጋግጠዋል፡፡
us_dollars
ከ20 ቀናት በፊት እያንዳንዱ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የውጭ ምንዛሬ ይሸጥ እንደነበር የተናገሩት ምንጮች፣ ከ20 ቀን ወዲህ ግን በሁሉም የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ማንኛውም አይነት የውጭ ምንዛሬ እንዳይሸጥ በደብዳቤ (cercular ዞሯል) ተከልክሏል፡፡

በመሆኑም አሁን ላይ ዜጎች በውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደተቸገሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ‹‹በተለየ ሁኔታ የሚሸጥላቸው ሰዎች ከጉዞ ወኪላቸውና ከበላይ አካል ይዘውት በሚመጡት ደብዳቤ መሰረት ብቻ ነው ምንዛሬ ሊያገኙ የሚችሉት፡፡ ከዚህ ውጭ ግን እንደበፊቱ ማንም የውጭ ምንዛሬ ማግኘት አይችልም›› ሲል አንድ የንግድ ባንክ ሰራተኛ ገልጹዋል፡፡

የውጭ ምንዛሬ እጥረቱ የተከሰተው በዶላር ምንዛሬ ብቻ ሳይሆን በሁሉም የውጭ ምንዛሬዎች ላይ መሆኑንም ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡ አሁን ላይ አንድ የአሜሪካ ዶላር በጥቁር ገበያ እስከ 22 ብር እየተሸጠ እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል፡፡

በሌላ በኩል ከብሄራዊ ባንክ አካባቢ የደረሱት የነገረ ኢትዮጵያ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት መንግስት ቀደም ሲል በIMF የቀረበለትን የ‹ዲቫሊዌሽን› ጥያቄ መቀበሉ እንደማይቀር ታውቋል፡፡ ‹‹አሁን ያለው ሁኔታ እንደሚያሳየን መንግስት የብርን ዋጋ በቅርቡ ‹ዴቫሉዌት› ማድረጉ አይቀሬ መሆኑን ነው፡፡ አንዳንድ ‹አርቲፊሻል› የውጭ ምንዛሬ እጥረቶች ቢኖሩም ዋናው የችግሩ መነሻ ግን የ‹ዴቫሊዌሽኑ› ጉዳይ ነው›› ሲሉ የብሄራዊ ባንክ የኢኮኖሚ አጥኚው ለነገረ ኢትዮጵያ አስረድተዋል፡፡

ሰሞኑን መንግስት ለወራት ተከልክሎ የነበረው የአረብ ሀገራት የስራ ጉዞ እንደገና እንዲጀመር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም መናገራቸው አይዘነጋም፡፡ ይህም ወደ አረብ ሀገራት የሚሄዱ ዜጎች ተጨማሪ ምንዛሬ እንዲያስገኙ ከማሰብ ሳይሆን እንደማይቀር ይገመታል፡፡

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር “የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ እራስህን ከወያኔ አሽከርነት(መጠቀሚያነት) ልታርቅ ይገባል”አለ

$
0
0

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)


በህዝብ ላይ የሚደርሰው ጭቆናና እርዛት እስከመቼ?

ከኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ የተሠጠ መግለጫ

የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት ዘወትር ስልጣናቸውን ለማራዘም ካላቸው ነቢራዊ ፍላጎት የተነሳ በህዝብ ላይ ግድያ እና እስር ከመፈፀም አልፈው ሐገራችን ኢትዮጵያን ከማትወጣበት ማጥ ውስጥ ለመክተት ደፋ ቀና እያሉ ነው፡፡ በቅርቡ እንኳን በአሶሳ ከተማ ንፁሀን የትግራይ ወጣቶች ማንነታቸው እስካሁን ባልታወቁ ታጣቂዎች ተገድለዋል ይኸውም መንግስትእየተከተለው ብልሹ የዘውግ አስተዳደር ዋጋ እያስከፈለ መሆኑ እየታየ ነው በሌላ በኩል ይህ ግድያ መንግስት እራሱ የትግራይ ህዝብን ከጎኑ ለማሠለፍ በማሠብ እንደገደላቸው ግምታቸውን አስቀምጠዋል እንደምክንያት የጠቀሱት ምርጫ 97ን ተከትሎ በተነሳው ተቃውሞ መንግስት ተቃውሞውን ለማባባስ ፈረንሳይ ለጋሲዮን ከቀድሞዋ የትምህርት ሚኒስቴር ወ/ሮ ገነት ዘውዴ ግቢ ወደውጭ ቦንብ በመወርወር 6 ፖሊሶችን በመግደል ፖሊሶችን ለማነሳሳት እና ህዝቡን ለማሳሳት ቢሞክርም በመጨረሻ ጉዳዩን የአሜሪካ ኤምባሲ ይፋ ሲያወጣው የመንግስት ሴራ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ የአሶሳው፣ የአምቦው፣ የጎንደሩ እና የወለጋው ግድያም ከዚህ የተለየ አይሆንም፡፡

የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴም ለመንግስት እና ለህዝቡ የሚከተለውን መልዕክት ማስተላለፍ ይወዳል፡፡

የመምህራኑ መልዕክት ለመንግስት

ማንኛውም መንግስት ህዝቡን ማዳመጥ ይኖርበታል መንግሥት ሕዝብን የሚያዳምጠው በሕገ መንግሥቱ ስለሚገደድ ብቻ መሆን የለበትም፡፡ የሕዝብ ወገን ነኝ የሚል ሥልጣን የያዘ ፓርቲና መንግሥት፣ ሕዝብን ምረጠኝ የሚል ፓርቲና መንግሥት፣ የሕዝብ ከበሬታና አመኔታ ሊያገኝና ዓላማውን በተግባር ላይ ሊያውል የሚችለው ሕዝብን ሲያዳምጥ ብቻ ነው፡፡ ሥልጣን ላይ የሚቆየው ሕዝብን ሲያዳምጥ ብቻ ነው፡፡ ሕዝብን ማዳመጥ ለራስ ተብሎም መደረግ ያለበት ነው፡፡ የማያዳምጥ መንግሥት የማይደመጥ መንግሥት ይሆናልና፡፡
የመምህራኑ መልዕክት ለኢትዮጵያ ህዝብ

የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ ለሐይማኖትህ፣ ለሐገርህ እና ለቀጣይ ትውልድ አስበህ እራስህን ከወያኔ አሽከርነት(መጠቀሚያነት) ልታርቅ ይገባል፡፡ መንግስት ህዝቡ ፊቱን ካዞረበት እና ካልተገዛለት ማንንም ሊገዛ እንደማይችል የቅርባችን የጋዳፊ አገዛዝ ምስክር ነው፡፡ ስለሆነም ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ከኢህአዴግ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት መመስረት የለብንም ከዚያም አልፎ ከወያኔ ጋር ተለጥፈው ህዝባቸውን የሚያስወጉ ጎረቤቶቻችንን ጭምር ከማንኛውም ማህበራዊ ህይወት በማግለል ትምህርት ልንሠጣቸው ይገባል፡፡

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!!!!!!!!!!!
የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

የወላይታ ዞን የአንድነት አመራሮች በመንግስት ሀይሎች ከባድ ድብደባ ተፈፀመባቸው

$
0
0

(ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ) የወላይታ ዞን የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ እና የዞኑ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ወኖ በዳሳ ትላንት ጥቅምት 22 ቀን 2007 ዓ.ም ከቀኑ በ 8 ሰዓት ከስብሰባ ወጥተው በወላይታ ሶዶ ከተማ በአንድ ሆቴል ውስጥ እያሉ በከተማው የፖሊስ አዛዥ መመሪያ በመንግስት ሀይሎች “እኛ ሀገር እመራን እናንተ ትቃወሙናላችሁ እናንተን እናጠፋቹሀለን” በማለት ከባድ ድብደባ እንደተፈፀመባቸው የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ለፍኖተ ነፃነት አስታወቀ፡፡ አመራሮቹ በድብደባው ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ታውቋል፡፡
UDJ
በድብደባው ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው አቶ ወኖ በዳሳ ራሳቸውን ስተው በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ቢወሰዱም እስካሁን እንዳላገገሙ እና የዞኑ የአንድነት ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ ህክምና አግኝተው ከወጡ በኋላም በከተማው ደህንነቶች ክትትልና ወከባ እየደረሰባቸው እንደሚገኝም ታውቋል፡፡
የወላይታ ዞን የአንድነት አመራሮች ላይ ድብደባ እንዲደርስ መመሪያ የሰጡት የከተማው የፖሊስ አዛዥ በአቶ ወኖ ላይ በደረሰው ከባድ ጉዳት ተደናግጠው በአምቡላንስ እንዲወሰዱ ካደረጉ በኋላ የዞኑ የአንድነት ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ “በአንድም ሚዲያ ስለሁኔታው እንዳይናገሩ” በሚል ክትትል እያስደረጉባቸው ያገኛል፡፡

ዶ/ር ኑሮ ደደፎ “ጀነራል ከማል ገልቹ ከኔ በላይ ሕግ የለም፤ ከኔ በላይ ሰው የለም በማለታቸው ከሥልጣን ተነስተዋል”አሉ

$
0
0

አዲሱ የኦነግ መሪ ዶ/ር ኑሮ ደደፎ በላስቬጋስ ከተማ ከሚሰራጨው ሕሊና ራድዮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ እነሆ፦

ዶ/ር ኑሮ ደደፎ “ጀነራል ከማል ገልቹ ከኔ በላይ ሕግ የለም፤ ከኔ በላይ ሰው የለም በማለታቸው ከሥልጣን ተነስተዋል”  አሉ

በአፋር ክልል ዱብቲ ከተማ አንድ ወጣት ባልታወቁ ኃይሎች ተገድሎ ተገኘ

$
0
0

አኩ ኢብን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው፦
afar kilil
በአፋር ክልል በዱብቲ ከተማ አንድ ወጣት ተገድሎ ተገኘ። ከሁለት ሳምንታት በፊት በዱብቲ ከተማ ሲዒድ አባተ የተባለ ወጣት ባልታወቁ ኃይሎች በከፉኛ ተደብድቦና ተገድሎ መገኘቱን ከቦታው ዘግይቶ ዛሬ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ግድያውን የፈፀሙትን አካላት እሰካሁን አልተያዙም።

ሲዒድ አባተ አፋር ባይሆንም በዱብቲ ከተማ ተወልዶ ያደገና በዱብቲ ወጣቶች ዘንድ የሚወደድ ልጅ እንደነበረ አንዳንድ የዱብቲ ነዋሪዎች የሆኑ አብሮ አደጎቹ ያስረዳሉ። የዱብቲ ከተማ ፖሊስም የዚህ ወጣት ህይወት ማትረፍ እንዳልቻሉና ወንጀለኞችን ፈልጎ ለህግ ለማቅረብ በመጠነኛ መልኩም የጣሩ ቢሆንም እሰካሁን አልተሳካም። አሁንም በከተማዋ የሚኖሩ ነዋሪዎች ለህይወታቸው እንደሚሰጉ ይናገራሉ።

በዚህ ጉዳይ ላይ የዱብቲ ከተማ የፖሊስ ኮሚሽን ጽ/ቤት አስተያየት ለማካተት ያደረኩት ሙከራ አልተሳካም ።

ሲዒድ ላይ በተፈፀመው ግዲያ በጣም ማዘናችንን እየገለፅን ለወዳጅ ቤተሰቦቹ መፅናናትን እንመኛለን ።

የህገ ወጡ መጅሊስ አባላት እና ሲቪል ፖሊሶች ባዩሽ መስጂድን ለመንጠቅ ሙከራ ማድረጋቸው ታወቀ!

$
0
0

bayush mosque
ድምፃችን ይሰማ እንደዘገበው፦

የህገ ወጡ መጅሊስ አባላት እና ሲቪል ፖሊሶች ባዩሽ መስጊድን ለመንጠቅ ሙከራ ማድረጋቸው ታወቀ::

ዛሬ ረፋዱ ላይ የህገ ወጡ መጅሊስ አባላት፣ ሲቪልና ፌደራል ፖሊሶች፣ እንዲሁም ወደሃያ የሚጠጉ በእድሜ የገፉ ሴቶች አንድ ላይ በመሆን የሴቶችን መስጂድም ጭምር በማስከፈት ወደመስጂዱ በመግባት ቦታውን የተቆጣጠሩ ሲሆን በመስጂዱ የሚገኙትን ቁርአኖችም ቆጥረው ‹‹መስጂዱን እናሽገው? አናሽገው?›› በሚል እርስ በእርስ መጨቃጨቃቸውን የዓይን ምስክሮች ገልጸዋል፡፡ በመስጂዱ የነበረው ሙስሊም በወቅቱ በዝምታ ጉዳዩን ሲከታተል የቆየ ሲሆን የዝሁር ሰላት ሰዓት ሲቃረብም ያለማይክራፎን አዛን ተደርጎ ተሰግዷል፡፡

ሁኔታው በዚሁ መልኩ እስከ 9 ሰዓት ከቆየ በኋላ ሰዎቹ የላይኛውን መስጂድ አሽገው ቦታውን ለቅቀው የሄዱ ሲሆን በህገ ወጥ ተግባራቸው የተቆጣውና ዝሁር ሰላቱን ታግሶም ቢሆን የሰገደው የአካባቢው ህዝበ ሙስሊም ግን አስር ሰላት ሲደርስ ሰላት የማይቀር አምልኮ ነውና መስጂዱን ከፍቶ የተለመደ ዒባዳውን ለመቀጠል መገደዱ ታውቋል፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃዎች ሲገኙ የምናሳውቅ ይሆናል::

ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል::
ድምፃችን ይሰማ::


በተለያዩ ክልሎች ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባችሁን አውልቁ በሚል ከትምህርታቸው እየተፈናቀሉ ነው

$
0
0

በአሶሳ እና በሽሬ እንደስላሴ ከተማ የሚኖሩ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃባችሁን አውልቁ በሚል ከትምህርት ገበታቸው እየተፈናቀሉ እንደሚገኙ ተገለፀ::

አቡ ዳውድ ኡስማን

በቤኒሻንጉል ጉምዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በአሶሳ ከተማ በሚገኙ የ1ኛ ደረጃ ት/ቤት የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው መማር እንዳይችሉ እየተደረጉ መሆናቸውን ምንጮች አስታወቁ፡፡

ፎቶ ከፋይል

ፎቶ ከፋይል

በአሶሳ ከተማ በሚገኙ ት/ቤቶች ውስጥ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው በትምህርት ገበታቸው ላይ መገኘት እንደማይችሉ የት/ቤቱ አስተዳደሮች እየከለከሏቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

በቤኒሻንጉል ጉምዝ በአሶሳ ከተማ በሚገኝ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት 35 የሚሆኑ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባችሁን ካላወለቃችሁ መማር አትችሉም በመባላቸው ከትምህርት ገበታቸው መፈናቀላቸውን ምንጮች አስታውቀዋል፡:

የትምህርት ቤቱን ርዕሰ መምህርን በጉዳዩ ላይ ለማነጋገር በአሶሳ ከተማ በስፋት በህዝብ ዘንድ የሚታወቀው ሰለፊያ ተብሎ የሚጠራው መስጂድ ኮሚቴዎች ሙከራ ያደረጉ ሲሆን ርዕሰ መምህሩ “እናንተ አሸባሪዎች እስካሁን አላቹ እንዴ” በማለት የተሳለቀባቸው ሲሆን ሴት ተማሪዎቹ ሂጃባቸውን እስካላወለቁ ድረስ በትምህርት ገበታቸው ላይ እንደማይቀጥሉ ምላሽ እንደሰጣቸው ታውቋል፡፡

በተመሳሳይም በትግራይ ክልል በሽሬ እንደስላላሴ ከተማ በሚገኙ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ውስጥ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው መማር እየተከለከሉ መሆናቸውን ምንጮች ዘግበዋል፡፡

በበሽሬ እንደስላሴ ከተማ የሚኖሩ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባችሁን አውልቃችሁ ተማሩ በመባላቸው ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለው በቤት ውስጥ ተቀምጠው እንደሚገኙ ታውቋል፡፡

የትምህርት ቤት አስተዳደሮች የተማሪዎችን ወላጆች በመሰብሰብ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገሩ ሲሆን ወላጆችን እና ተማሪዎችን ሲያስፈራሩ እንደነበር ተዘግቧል፡፡

በመላው ሃገሪቱ የሙስሊሞች ዋነኛ የእምነታቸው መገለጫ የሆነውን ሂጃብ እንዲያወልቁ ለማድረግ በመንግስት በኩል ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡ የፌደራል ጉዳዬች ሚኒስተር ዶ/ር ሽፈራው በኢስላም ላይ ባላቸው የግል ጥላቻ በመነሳት ከመሰሎቻቸው ጋር በመቀናጀት ሙስሊም ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ለማፈናቀል በክፍተኛ ደረጃ እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ የሚታወቅ ሲሆን በመላው ሃገሪቱም በሴኩላሪዝም ሽፋን ሙስሊሞች ትምህርታቸውን አልያም ሃይማኖታቸውን እንዲመርጡ በማስገደድ ሙስሊሙን ከትምህርት ገበታ ለማራቅ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡

ሂጃብ የሙስሊም ሴት ህልውናዋ እንጂ ለድርድር የሚቀርብ የፖለቲካ አጀንዳ አይደለም።

‹‹ጥቁሩ አብዮት›› እና ኢትዮጵያ

$
0
0


ጌታቸው ሺፈራው

ከሳምንታት በፊት ከጓደኞቼ ጋር እስክንድር ነጋን ልንጠይቀው ወደ ቃሊቲ አቅንተን ነበር፡፡ በወቅቱ ስለ ለውጥ አውርቶ የማይጠግበውን እስክንድርን ስለ ኢትዮጵያ መጻኢ እድል ስንጠይቀው የመለሰልን ቀላል ግን ደግሞ የሚገርም መልስ ነበር፡፡ እስክንድር ተስፋ አስቆራጭ የሚመስለው ትግል ፍሬያማ ሊሆን እንደሚችልና በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚነሳው ጥያቄን ልክ እንዲህ ነበር ያስረዳን፡፡
black spring burkinafaso
‹‹እነ ጋናን፣ ዛምቢያን፣ እና ሌሎቹንም የአፍሪካ አገራት ነጻ እንዲወጡ ኢትዮጵያ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጋለች፡፡ አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት አሁን ነጻ ካወጣቻቸው ኢትዮጵያ የተሻለ ዴሞክራሲ ገንብተዋል፡፡ እኛ እየጠየቅን ያለነው እንደነዚህ አገራት አይነት ስርዓት እንዲሰፍን ነው፡፡ የቅንጦት ጥያቄ አልጠየቅንም፡፡ መጠየቅ ከነበረብን እጅግ ትንሹን ነው እየጠየቅን ያለነው፡፡››

ከሶስት ቀናት በፊት እስክንድር እኛ ነጻ አውጥተናቸው ከእኛ ይሻላሉ ካላቸው አገራት መካከል ቡርኪናፋሶዎች ለስርዓቱ ሌላ ጥያቄ አንስተው ራሳቸው ሲመልሱት ስመለከት ያስታወስኩት እስክንድርን ነው፡፡ እኛ ምንም ጥያቄዎች ሳይመለስልን እነሱ ሌላ ጥያቄዎችን እያነሱ እራሳቸው መመለሱን ተያይዘውታል፡፡

ቡርኪናፋሶ ምንም እንኳ እንደ አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት ድሃ ብትሆንም እንደ እኛ 6ና 7 ሚሊዮን ህዝብ አይራብባትም፡፡ ምንም እንኳ እስከ ትናንትና ድረስ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ላይ የተቆናጠጠ መሪ ያስተዳድራት የነበር ቢሆንም ፓርቲዎችና ህዝቡ ሀሳቡን የሚያንጸባርቅባቸው ሚዲያዎችና ሌሎች ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ዘርግታለች፡፡ ገና እ.ኤ.አ በ1990 ጀምሮ ሬድዮና ቴሌቪዥንን በግል በመያዛቸው ህዝቡ ለአማራጭ ሚዲያ ቅርብ ነው፡፡ ኢንተርኔት ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚደረገው በስርዓቱ አይታፈንም፡፡ ቡርኪናፋሶ እንደ ኢትዮጵያ ጋዜጠኞች በጅምላ እስር ቤት የሚታጎሩባት፣ በገዥው ፓርቲ ጫና የሚሰደዱባት፣ ሚዲያዎች የሚታፈኑባትና የሚዘጉባት አገር አይደለችም፡፡

ባለፉት አመታት ለአጭር ጊዜ ከሶስት የማይበልጡ ጋዜጠኞች ታስረዋል፡፡ ባለፉት 20 አመታት በሚዲያው ታሪክ አስከፊው የሚባለው የአንድ ጋዜጠኛ ባልታወቁ ሰዎች መገደል ብቻ ነው፡፡ በቡርኪናፋሶ ያለፉት 20 አመታት ታሪክ ውስጥ በሚዲያው ጠባሳ ነጥብ ተደርጎ የሚወሰደውና የውጭ ተቋማት ጫና ለማሳደር የሚጥሩበት ጉዳይም የዚህ ጋዜጠኛ ሞት ነው፡፡ ከአምስት አመት በፊት አንድ ጋዜጠኛ የ‹‹እንገድልሃለን›› ማስፈራሪያ ስለደረሰበት ዓለም አቀፍ የጋዜጠኛ ማህበራት አሁንም ድረስ ስርዓቱን በመውቀሻነት ይጠቀሙበታል፡፡ በቡርኪና ፋሶ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብሰባ እንዳያደርጉ፣ ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይወጡ አይከለከሉም፡፡ የአገሪቱ ሲቪክ ማህበራት ኢህአዴግ መራሹ ‹‹መንግስት›› ስር ካሉት የተለዩ ናቸው፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በሽብር ስም ወህኒ አይወረወሩም፡፡ በአጭሩ ቡርኪናፋሶ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚጠየቁትን አብዛኛዎቹን የፖለቲካ ጥያቄዎች መልሳለች፡፡

ምንም እንኳ ቡርኪናፋሶ ከእኛ የተሻለ፣ እኛ የምጠይቀውን ጥያቄ የመለሰች ቢሆንም፣ ፖለቲካዊ ስርዓት ብትገነባም በሚፈለገው መንገድ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ሰፍኖበታል ለማለት ግን አያስደፍርም፡፡ ቡርኪናፋሶን ለባለፉት 27 አመታት ያስተዳደሩት ፕሬዝደንት ብላይሴ ኮምፓሬ ወደ ስልጣን የመጡት ተወዳጁን የቀድሞ የአገሪቱን ፕሬዝደንት ቶማስ ሳንካራን አስገድለው ነው፡፡ የገዳዮቹ ቻርለስ ቴለርና ሙአመድ ጋዳፊ የቅርብ ጓደኛም እንደመሆናቸው ለህዝቡ ምቹ ናቸው ማለት አይቻልም፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሶሻሊስት ከነበረው ቶማስ ሳንካራ የተለየ ሆነው በመገኘታቸው የምዕራባውያን ተላላኪ ሆነው አገልግለዋል፡፡ በተለይ የምዕራብ አፍሪካን አለመረጋጋት ለመቆጣጠር ፈረንሳይና አሜሪካ ቡርኪናፋሶን ተጠቅመውበታል፡፡

እ.ኤ.አ በ1991፣ በ1998፣ በ2005ና 2010 በተደረገው ምርጫ አሸነፍኩ ቢሉም ያልተዋጠላቸው በርካቶች እንደነበሩ ይነገራል፡፡ በፕሬዝዳንትነቱና በፓርቲያቸው ደስተኛ ያልሆኑት ቡርኪናፋሶውያን እ.ኤ.አ በ2011 በርካታ አመጾችን አስነስተው ስርዓቱን አስደንግጠዋል፡፡ ለአብነት ያህል በዚሁ አመት ሰራዊቱ ደሞዜ አልተከፈለኝም ብሎ የጀመረው አመጽ ፕሬዝደንቱ ወደ ተወለዱበት መንደር እንዲደበቁ አስገድዷቸው ነበር፡፡ የህገ መንግስቱ መሻሻል ሀሳብ የቀረበው ከአመት በፊት ሲሆን ተቃሞው ገጥሞት እንደገና ተቋርጦ ቆይቷል፡፡

ከእኛ አገር የተሻለ ግን ደግሞ መሻሻል በነበረበት የቡርኪናፋሶ ዴሞክራሲ ውስጥ ህዝቡ ጥያቄውን ሲያቀርብ ቆይቶ ሰሞኑን አቅሙን አሳይቷል፡፡ ቶማስ ሳንካራን ያህል ተወዳጅ መሪ አስገድለው ስልጣን ላይ የወጡትን ፕሬዝዳንት በሰዓታት ውስጥ ማፍረክረክ ችሏል፡፡ የገዥው ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት፣ ቴሊቪዥን ጣቢያው፣ ፓርላማው፣ የባለስልጣናትን ቤትና ሌሎችም የመንግስት ቢሮዎች በመቆጣጠርና በእሳት በማጋየት የጀመረው የተቃውሞው ጎራ የአንድ ቀን ውሎ ህገ መንግስቱን በማሻሻል ስልጣናቸውን ለማራዘም ደፋ ቀና ሲሉ የነበሩት ፕሬዝዳንት ‹‹መንግስትን አፍርሸዋለሁ፡፡ መልዕክቶቻችሁን ሰምቻለሁ፡፡ የሽግግር መንግስት ይቋቋማል›› ብለው የተለየ አቋም እንዲይዙ አስገድዷቸዋል፡፡ ከዛ በፊት ብዙም ቁብ ሰጥተዋቸው ያልነበሩትን ተቃዋሚዎች ‹‹አመጹን እንድታቆሙ እለምናለሁ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ከሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ጋር በመወያየት ችግሩን መፍታት አለብን›› ብለው እንዲማጸኑ ግድ ሆኖባቸዋል፡፡ በስተመጨረሻም በአንድ ቀን የህዝብ አመጽ ስልጣን መልቅቃቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡

በቡርኪናፋሶው ገዥ ፓርቲ ላይ የተነሳው አመጽ ሰራዊቱንም ጭምር ያሰባሰበ ሲሆን ቀድሞው የጦር ሚኒስትር ጀኔራል ኩአሜ ሎውጉን ጨምሮ በርካቶች ሰላማዊ ታጋዮችን ተቀላቅለዋል፡፡ ፓርላማ፣ የመንግስት መስሪያ ቤቶችንና የባለስልጣናቱን ቤት ባነደደው እንቅስቃሴ የሞቱት ሰዎች ጥቂቶች እንደሆነ የታወቀ ሲሆን ይህም መከላከያና፣ ፖሊስና ደህንነቱ ከህዝብ ጎን እንደቆመ በግልጽ አሳይቷል፡፡

ከኡጋዱጉ ወደ አዲስ አበባ?

የአረቡ የጸደይ አብዮት በተነሳበት ወቅት ጂቡቲ፣ ሱዳን፣ ዚምባብዌ፣ ማዕከላዊ አፍሪካና ሌሎችም አምባገነኖች ስልጣን ላይ የተቆናጠጡባቸው አገራት ውስጥ ጅምር እንቅስቃሴዎች ተስተውለው ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ ምንም አይነት እንቅስቃሴ ባልታየበት ስለ ጸደይ አብዮት ያወሩት እነ እስክንድር በሽብርተኝነት ስም 18 አመት ተፈርዶባቸው የእርስ ቤት በር ተቆልፎባቸዋል፡፡ ይህን አብዮት ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲከሰት ያደርጋሉ ተብለው የተፈሩ በርካታ የታዋሚ ፓርቲ መሪዎችና ጋዜጠኞም በተመሳሳይ መልኩ ለዘመናዊ ግዞት ተዳርገዋል፡፡

የአረቡን አብዮት ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲከሰት ያደርጋሉ ብሎ በርካቶችን የሚያስረው ስርዓቱ በአንድ በኩል የዓረቡ አብዮት ኢትዮጵያ የማይደገምባቸው የሚላቸው ምክንያቶችን በማስቀመጥ፣ በሌላ በኩል ለኢትዮጵያ በእጣ ፈንታ እንደማያዋጣ በማስመሰል ህዝብን ለማሳመን ጥሯል፡፡ ይህ ሁሉ የስርዓቱ ተቃርኖ የህዝቡን ጥያቄ መመለስ ካለመቻሉ የመጣ መደነባበርና ግራ መጋባት እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ በተለይ ስራ አጥነት፣ ሙስና፣ አፈና፣ በአረቡ ዓለም በስፋት የታየና ለአብዮቱም ዋነኛ ምክንያት እንደነበር የሚያውቀው ህወሓት/ኢህአዴግ ኢትዮጵያውያን ያሉበት ተመሳሳይ ሁኔታ እንቅልፍ ቢነሳው የሚገርም አይሆንም፡፡

የአረቡ ዓለም አብዮት ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት የለውም ሲባል ኢትዮጵያ ከሰሜን አፍሪካ ይልቅ ከሰሃራ በታች ለሚገኙት የአፍሪካ አገራት ቅርበት እንዳላት የሚያመለክት ነው፡፡ ግን አሁን ደግሞ በቡርኪናፋሶ ያ ገዥዎቹን እንቅልፍ የሚነሳው ውሽንፍር ተነስቷል፡፡ እንዲያውም ከእኛ በተሻለ ፖለቲካ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ላይ የምትገኝ አገር ውስጥ፡፡

60 በመቶ የሚሆኑት ቡርኪናፋሶውያን ወጣቶች ናቸው፡፡ ኢትዮጵያም ከዚህ ያላነሰ ደግሞም ስራ አጥ፣ በሙስና፣ በአስተዳደራዊ በደል፣ በአፈና አሳሩን የሚያይ ወጣት አገር ነች፡፡ ቡርኪናፋሶውያን እ.ኤ.አ በ2011 አመጽ ወጥተውበት ከነበረው የኑሮ ውድነት በላይ ኢትዮጵያውያን ላለፉት 10 አመታት በዚህ በገዥው ፓርቲ የበላይነት የሚመራው የፖለቲካ ኢኮኖሚያ ካመጣው ጣጣ ጋር ከርመዋል፡፡

የሙስሊሙ፣ ኦርቶዶክሱ፣ ኦሮምኛ፣ አማርኛ፣ ትግርኛ…. ተናጋሪው በአሸባሪነት ሆነ በሌላ ስም እስርና ስቃይ እጣ ፈንታው ሆኗል፡፡ ጋዜጠኞች ስርዓቱ በሚያሳርፍባቸው በትር በጅምላ አገር ለቀው እየተሰደዱ ነው፡፡ መከላከያው ስርዓቱ ካመጣው በማንነት የመከፋፈል አባዜ ባሻገር በሌሎች ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥያቄዎች እንደተወጠረ በየጊዜው የሚወጡት መረጃዎች ዋቢዎች ናቸው፡፡ የኤርትራ ተቃዋዎች ሰፋፊ ቢሮዎች ተሰጥቷቸው ሲፈልጉ ሰለማዊ ሰልፍ፣ ሲፈልጉ ስብሰባ በሚያደርጉበት አገር የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በገዛ አገራቸው ጽ/ቤት ከማግኘት ጀምሮ፣ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ፣ ወረቀት መበተን ቅንጦት ሆኖባቸዋል፡፡

በእርግጥ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲህ ተርፎ የፈሰሰው ግፍ ቱኒስ ላይ የተነሳውን የአረቦችን አብዮት አዲስ አበባ ላይ ይደግማል ተብሎ በመፈራቱ በርካቶች ታስረዋል፡፡ መስቀል አደባባይ ‹‹የኢትዮጵያውያን ታህሪር›› እንዳይሆን በመፈራቱ የኃይማኖት በዓላትና የኢህአዴግ የድጋፍ ሰልፎች ውጭ ተቃዋሚዎች ዝር የማይሉበት ክልክል ቦታ ሆኗል፡፡

የሰሜን አፍሪካ ጎዳናዎች በወጣቶች በተሞሉበት ጊዜ ኢትዮጵያውያን ለዚህ አብዮት ሞተር ከሆነው የማህበራዊ ሚዲያ ጋር የነበራቸው ትውውቅ ከአሁን ካለው አንጻር አነስተኛ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ህዝቡ ውስጥ የነበረው የኢኮኖሚ ችግር ከጊዜ ወደ ጊዜ ከመባባስ ውጭ የተለየ መፍትሄ አልተሰጠውም፡፡ የህዝብ አገልግሎት ከመቆራረጥ ወደ መጥፋት በመሸጋገሩ ህዝብ በራሱ ሰላማዊ ሰልፍ እስከመውጣት ደርሷል፡፡ የሽሮ ሜዳ ነዋሪዎችን ያስታውሷል!

ቡርኪናፋሶ ውስጥ ስርዓቱን በሁለት ቀን ያስወገዱት ወጣቶች ከ1500 አይበልጡም፡፡ ከዚህ አንጻር በኢትዮጵያ በተቃውሞ ጎራ ያለው ሳይጨምር አርብ አርብ መስጊዶችን በተቃውሞ ሲሞሉት የታዩት ሙስሊሞች ብቻ ለውጥ ሊያመጡ እንደሚችሉ የሚያጠራጥር አይሆንም፡፡ ተቃዋሚዎች የተበታተኑና የፋይናንስ አቅም የሌላቸው በመሆናቸው ኢትዮጵያ ካለው የተቃዋሚ ሁኔታ የተለየ ነገር አይታይባቸውም፡፡ ሆኖም ሰላማዊ ሰልፍም ሆነ ስብሰባ የማድረግ፣ በሚዲያዎች ሀሳባቸውን በመግለጽ ከኢትዮጵያ የተሻለ አጋጣሚ ነበራቸው፡፡

የቡርኪናፋሶው ገዥ ፓርቲ 27 አመት ሲቆይ ህዝብ ደስተኛ ሆኖ አይደለም፡፡ ከዚህ ይልቅ ከኢትዮጵያው ጋር የማይነጻጸር ቢሆንም ከምዕራባውያን ጋር ባለው ግንኙነትና በፈርጣማ ክንዱ ስልጣን ለማስጠበቅ የሚችለውን ሁሉ አድርጓል፡፡ በእነዚህ ሁሉ አመታት ህዝብ ደስተኛ ባይሆንም በሁለት ቀን ይህን ያህል ለውጥ ያመጣል ብሎ የገመተው ግን አልነበረም፡፡ የቡርኪናፋሶ ሁኔታ አፈናም ሆነ በምዕራባውያን ተላላኪነት ራሱን ለማቆየት የሚጥር ስርዓት በህዝብ ኃይል በአጭር ጊዜ ሊሸነፍ እንደሚችል የቅርብ ጊዜ ምስክር ሆኗል፡፡ በተቃውሞው ጎራ ድካም፣ በአፈናው ብዛት እስካሁን ቡርኪናፋሶውያን ያገኙትን መብትና ጥቅም ማግኘት ያልቻለው የኢትዮጵያ ህዝብ በስርዓቱ ላይ ይህ ነው የሚባል ጫና ሊያደርግ እንደማይችል የሚገምቱት ብዙዎቹ ናቸው፡፡

ነገር ግን ሙስሊም፣ ክርስቲያን፣ መምህራን፣ መከላከያ ሰራዊት፣ የራሱ አባል ድርጅቶች ጋር መስማማት ያልቻለው የኢትዮጵያ ገዥው ፓርቲም በህዝብ የሚፈተን ለመሆኑ ትናንት እነ ጋዳፊ፣ እነ ሙባረክና ቤን አሊ ላይ ከታየው ባሻገር የዛሬው የቡርኪናፋሶው ህዝብ ድል ትልቅ ምስክርነት ይሰጣል፡፡ በቱኒስ የተነሳው ለውጥ ከቱኒዚያ ከተሞች አልፎ የግብጹን ታህሪር፣ ትሪፖሊና ሌሎች የሊቢያ ከተሞችን እንዳጥለቀለቀው፣ ስርዓትም እንደለወጠ ሁሉ ኡጋዱጉ ከሚገኘው ፓርላማ የተነሳው እሳትም አገሪቱ ውስጥ የነበረውን የስርዓቱ ቆይታ አውድሞታል፡፡

ጽሁፉን በእስክርንድ እንደጀመርኩት በእሱው መደምደሚያ መጨረስ ወደድኩ! ‹‹በሰሜን አፍሪካው አብዮት እንቅስቃሴዎቹ የተቀጣጠሉት በዋና ዋና ከተማዎቹ ነው፡፡ እኛ አገርም ቢሆን ተመሳሳይ ነው የሚሆነው፡፡ አዲስ አበባ ላይ የሚፈጠር ለውጥ አጠቃላይ የአገሪቱን ፖለቲካዊ ሁኔታ ይቀይራል፡፡… ውሃ በ99ንኛው ዲግሪ ሴንቲግሬድ ነው የሚፈላው፡፡ እስከዛ ድረስ ምንም አይነት ለውጥ አይታይበትም፡፡ ውሃ የሚያፈላ ሰው 99 እስኪደርስ ድረስ ማህል ላይ ተስፋ ቆርጦ ሊተውው ይችላል፡፡ ግን 99 ዲግሪ እስኪደርስ ድረስ የራሱ የሆነ የማይታይ ለውጥ ያደርጋል፡፡ ተስፋ ያልቆረጠ በአንድ ዲግሪ ለውጡን ያየዋል፡፡››

ኦጋዱጉ ላይ ተስፋ ያልቆረጡት 1500 ወጣቶች የለውጡን የመሞቂያ ነጥብ ቀይረውታል፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ ኡጋዱጉ ላይ ካለው የከፋ ችግር ቢኖርም እስካሁን 99 ዲግሪ አልደረሰም! ይህ የመፍያ ነጥብ፣ የኡጋዱጉው ውሽንፍር፣ ከአረቡ ይልቅ ለኢትዮጵያ ይቀርባል የሚባለው የጥቁር አፍሪካ ‹‹ጥቁሩ አብዮት›› ወደ አዲስ አበባ መቼ ይደርሳል የሚለውን ለጊዜውም መገመት የሚቻል አልሆነም፡፡ ግን ጭቆና በተትረፈተፈበት አገር ለውጥ ተፈጥሯዊ ነውና ነገ፣ ሳምንት፣ የዛሬ ወር፣ አመት… መከሰቱ ግን የማይቀር ነው፡፡ ገዥዎቹ ለለውጥ ዝግጁ እስካልሆኑ ድረስ ቁጥሩ አንድ ሺህም ሆነ ሚሊዮን የለውጡን ዲግሪ ሴንቲግሬድ የሚቀይረው ሳይታሰብ አደባባይ ላይ የሚገኘው ህዝብ ነው!

ግልፅ ደብዳቤ፡ ለህጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ከምንም በፊት ብሔራዊ እርቅና ሃገራዊ መግባባት ዛሬውኑ ያሻናል

$
0
0

ብፁዓን አባቶቻችን !

እኛ ስማችንም ሆነ ምግባራችን ከንቱ የሆነ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ ፊት የሚያቀርብ አንዳች በጎ ምግባር የሌለን፣ ይልቁንም ይህን ሃገራዊ አጀንዳ ለማንሳት የማይገባን ታናናሾች ስንሆን፤ ይሁን እንጂ እንደ ማንኛውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምዕመን በፈጣሪያችንና በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ህያው ቃል በአደራ የተሰጠናችሁ ደካማ ልጆቻችሁ ነን፡፡
holy sinod excile
እኛ በማርቆስ ወንጌል በም. ፭ ከቁ. ፳፭-፴፬ እንደምናነባት አንዲት በደሟ ስትታጠብ እንደኖረችው ሴት፤ እንዲያ የተጨናነቀው የህዝብ ብዛት ሳያቆማት፤ ተሽሎክሉካ የመድሃኒቷን ልብስ በእምነት በመንካት ለ፲፪ አመታት ሲያሳቅቃትና ሲያሰቃያት ከነበረው ሸክሟ እንደነፃችው እንስት ያለን፤

አዎ! እኛ የሃገራችን እና የወገናችን ለዘመናት በትውልዶች የደም ጎርፍ መታጠብ ያሳቀቀን፣ መጭው ዘመን በእጅጉ ያስፈራንና ያስጨነቀን፣ በአንፃሩ ደግሞ በፈጣሪያችን እና በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መንበር ለተሰየማችሁት፣ በቅዱሳን ሐዋርያት እግር ለተተካችሁት፣ በቅዱሱ የእግዚአብሔር መንፈስ ወደ ምትመሩቱ ወደ ብፁዓን አባቶቻችን በማሳስባችን፤ ብሎም ጩኸታችንም ሰሚ ጆሮና እሩሩህ ልቦና ሲያገኝ ይህቺ በንፁሃን ልጆቿ የደም ጎርፍ የጨቀዬችው እናት ሃገራችንና ኢትዮጵያዊነታችን በፍፁም ሃገራዊ እርቅና የይቅርታ ምህረት እንደ አመዳይ እንደምትነፃ ፍፁም ተስፋ እና እምነት በልቦናችን የሰነቅን የዛች እንስት አምሳያዎች ነን፡፡

ብሔራዊ እርቅና መግባባት ለምን?
ብፁዓን አባቶቻችን !
በአለፉት ጥቂት ዓመታት እዚህ በስደት ሆነን ተለይተናቸው የኖርነውን የወላጆቻችንን ትውልድ በቅርበት ሆነን ለማወቅ እና በስደት የሚገፉትን የእርጅና ዘመናቸውንም ለመጋራት እግዚአብሔር እድሉን ሰጥቶናል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ለዘመናት ከእናቶቻችን እቅፍ ሳንወርድ ጀምሮ ስንኮመኩመው ያደግንበትን የዚያን ትውልድ እርስ በእርስ የመጠፋፋት ጀብዱ ከአፈ-ታሪክነት በአለፈ ደረጃ፤ የዚያን ዘመን የፖለቲካ እንቅስቃሴ በተለያዩ ተፃፃራሪ ጎራዎች ተሰልፈው ይዘውሩት የነበሩት “ታላላቅ” ሰዎች ያለፉበትን የታሪክ ጎዳና በመዋዕለ ዜናዎቻቸው ለአደባባይ በማዋላቸው፣ እኛም እነዚህን በንፁሃን ኢትዮጵያውያን ሰቆቃና የደም ጩኸት የታጨቁ ድርሳናት እንደዋዛ የማግኘትና የማንበብ እድል ለማግኘት ችለናል፡፡ በተጨማሪም አሁን ስልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ ባለስልጣናት በተለያዩ ምክንያቶች ከስርአቱ ተለይተው ከወጡ በኃላ የከተቧቸውን ዘገባዎች በቅርብ የማግኘት እድል ገጥሞናል፡፡

ከእነዚህ ህለቆ መሳፍርት በሌላቸው የንፁሃን ወገኖቻችን የሰቆቃ ጩኸቶች ከተሞሉ መዛግብት በተለይ የተረዳነው አንድ አብይ ጉዳይ አለ፡፡ ይሃውም በተለይም ከ፲፱፻፶ዎቹ ወዲህ እከሌ ከእከሌ ሳይባል እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ ህዝብ እጆቻችን በገዛ ወገኖቻችን ንፁህ ደም እንደ ተጨማለቀ እና ምድሪቱም በግፍ በፈሰሰው በልጆቿ ደም በእጅጉ እንደ ጨቀዬች ተረድተናል፡፡ ስለዚህም እኛና ምድሪቱ በአንድነት እንደረከስን፣ የወላጆች ቀሪ የእርጅና ዘመን በመሪር ሃዘን እንደተኮማተረ፣ የአእላፍትን ወገኖች የትዳር ጎጆ በሰቆቃ እንደተዘጋ፣ የንፁሃን ታዳጊ ህፃናትን ህይወት ከጅምሩ እንደጨለመ፣ ይልቁንም በዚህ ሁላችን በምናፍርበት እኩይ ምግባራችን በሰማይ በቅዱሳኑ ዘንድ ፍፁም እንደታዘነብን ይሰማናል፡፡
ቅዱሱ እግዚአብሄር በነብዩ በዮናስ መፅሃፍ በም. ፬ ከቁ. ፱-፲፩ “ . . . እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን ከማይለዩ ከመቶ ሃያ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ አላዝንምን? ” ይላልና ነው፡፡

ብፁዓን አባቶቻችን !
ለዚህም ሰቆቃና በደል ተጠያቂ የማይሆን ወይም አይመለከተኝም የሚል ኢትዮጵያዊ ማግኘት የሚቻል አይመስለንም፡፡ ከደሙ ንፁህ ነኝ የሚል ከተገኘም “ግመል በመርፌ ቀዳዳ…” ነው የሚሆንብን፡፡

ታዲያ ሁሉም በዳይና ተበዳይ በሆነበት ሁኔታ ለሁሉም ፍትህን በሚዛናዊነትና በርዕቱነት መስጠት የሚችል ምድራዊ ህግም ሆነ የፍትህ ተቋም ወይም ምድራዊ ዳኛ የምናገኝ አይመስለንም፡፡ በፍፁም እውነት የሚፈርድ እውነተኛ ዳኛ እንኳን ቢገኝ ማን ከሳሽ፣ ማን ተከሳሽ፤ ማን በዳይ ማንስ ተበዳይ ሊሆን ይሆን? እዚህ ላይ በዩሐንስ ወንጌል በም. ፰ ከቁ. ፩-፲፩ በተፃፈው የአመንዝራዩቱ ሴት ፍርድ ታሪክ ላይ ሁሌም የምናነባትንና ወደ እውነተኛው ፈራጅ ወደ ኢየሱስ ክርሰቶስ ፊት ለፍርድ የቀረበችውን እንስት እና ሊወግሯት የነበሩትን የከሳሾቿን ታሪክ ልብ ይሏል፡፡

እኛ ግን በአንድ የቀደመ ሃሳብ እንስማማለን፡፡ ይኃውም አስቀድሞ የገባንበት ታሪካዊ ፈተና የተገለጠላቸው ወገኖች ያለመታከት ደግመው ደጋግመው እንደሚያነሱት ሁሉ ብሔራዊ እርቅና ሃገራዊ መግባባት ከሁሉም የተሻለው የችግራችን መፍቻ መንገድ እንደሆነ እንረዳለን፡፡ ስለዚህም እኛም እንደ እነርሱ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ብሔራዊ እርቅ ይቅደም እንላለን፡፡

ማን ከማን ጋር ይታረቅ?
ብፁዓን አባቶቻችን !

ታራቂዎቹ እኛ ኢትዮጵያውያን ስንሆን የምንታረቀውም ከእራሳችንና ከፈጣሪያችን፣ ከምድር እና ከሰማይ ጋር ነው ብለን አናምናለን !
ሂደቱም ከሴት እስከ ከወንድ፣ ከትልቅ እስከ ትንሽ፣ ከጨዋ እስከ ምሁር፣ ከደሃ እስከ ባለፀጋ፣ ከፖለቲከኛ እስከ ገበሬ ወዘተ ሁላችንንም ያካተተ ሊሆን ይገባል የሚል ፅኑ እምነት አድሮብናል፡፡

ይሁንና ሁላችንም እንደምናውቀው ኢህአዴግን ወደ መንግስታዊ ስልጣን መምጣት ተከትሎ በነበረው ለውጥ ተስፋ የሰነቀው በውስጥም በውጭም የሚገኘው ህዝባችን በሃገራችን ብሔራዊ እርቅ እንዲወርድና ሁላችንም ወደ አንድ ሃገራዊ መግባባት እንድንደርስ፣ ሂደቱንም በወቅቱ በስልጣን ላይ ያለው አካል በቅንነት እንዲቀበለው እና ድጋፍ እንዲያደርግ ከፍተኛ የሆነ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፡፡

ነገረ ግን ሃገሪቱን እየመራ ያለው መንግስት ይቀርብለት ለነበረው ጥያቄ አሉታዊ እይታ ያለው እና ምላሹም ተስፋ የሚያስቆርጥ ስለነበረ እነሆ ሂደቱ በትንሹ ለአለፉት ፳፫ ዓመታት ምንም እመርታ ሳያሳይ በእንጥልጥል የሚገኝ እና ምንም አይነት ተስፋ ሰጪ ምልክቶች የማይታዩበት ለመሆን ተገዷል፡፡

ምንም እንኳ ዛሬም ድረስ ለዚህ ሃገራዊ አጀንዳ ተግባራዊነት በመትጋት እንቅልፍ የማይወስዳቸው ወገኖች እንደሚኖሩ ብንረዳም ከላይ በተገለፀው እንቅፋት ምክንያት ይህ ታሪካዊና ቅዱሱ የእርቅ እና የሰላም መንፈስ በጊዜ ህዝባችንና ሃገራችንን እንዳይታደግ ለጊዜው ስለተገታ ሌላ አማራጭ መፍተሄ የግድ መፈለግ እንዳለበት እናምናል፡፡ የእኛም አላማ አማራጭ የመፍትሄ አቅጣጫ ሊሆን ይችላል ያልነውን መንገድ ለመጠቆም ነው፡፡

መቼና የትስ ሆነን እንታረቅ?
ብፁዓን አባቶቻችን !

እዚህ ላይ “ማን ከማን ጋር ይታረቅ ከሚለው” ቁምነገር ጋር በዋናነት አብሮ መታሰብ የሚኖርበት ጉዳይ ሂደቱን አሁኑኑ የመጀመር አንገብጋቢነት ነው፡፡ ለምን ቢባል ጊዜን በመቅደም አላፊውን ትውልድ ከፍፁም የህሊና ሰላም ጋር ከመሸኘት፣ ወጣቱን አፍጦና አግጦ ሊውጠው ከሚጠብቀው የመጠፋፋት አዙሪት ለመታደግና፣ መጭውን ትውልድ ከደም ውርሱ ከማዳን አንፃር ሂደቱ ነገ ዛሬ ሳይባል በጊዜ መጀመር እንዳለበት በፅኑ እናምናለን፡፡

በሌላ መልኩ ደግሞ ሃገራችንን በቀደሙት ፲፯ ዓመታት ከመሩት ከቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዘደንት መንግስቱ ሃ/ማርያም እና ጓዶቻቸው ጀምሮ እስከ ዋነኛ ተቀናቃኞቻቸው ከነበሩት የመኢሶን ፣ የኢህአፓ ፣ የኢዲዮ ፣ የኦነግ፣ ወዘተ እስከ ዛሬዎቹ የኢህአዴግ አሳዳጆችና ተሳዳጆች ከነጓዶቻቸውና ደጋፊዎቻቸው በብዛት ከሃገራቸው ውጭ በስደት እንደሚኖሩ ተገንዝበናል፡፡
ስለሆነም ይህ የብሔራዊ እርቁ እና የሃገራዊ መግባባቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ እዚሁ በስደት ቢጀመር በመተላለቅ ዘመናቶቻችን ከመሪነት እስከ ተራ አባልነትና ደጋፊነት፣ በከፍተኛ ሁኔታ በብዛትና በንቃት ይሳተፍ የነበረውን የህብረተሰብ ክፍል በቀላሉ መድረስ የሚቻል ስለሚሆን፤ የመጀመሪያው ታሪካዊ ምዕራፍ በመላው ዓለም ተበትነን የምንገኝ ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ያካተተ ሆኖ ሊከናወን ይችላል ብለን እናምናለን፡፡ ከዚያም እግዚአብሔር ሲፈቅድ እና ጊዜው ሲደርስ ሂደቱ ወደ ሃገራችን ተሸጋግሮ በሃገር ውስጥ የሚገኘውን መላውን ህዝባችንን የሚያሳትፍ በመሆን ይጠናቀቃል የሚል ታላቅ ተስፋ አለን፡፡ በዚህም ጅማሮ በሃገር ቤት የሚገኘው ወገናችን ሂደቱ እንዲፋጠንና እርሱም ዘንድ እንዲደርስ ከፍተኛ ግፊትና አስተዋፅኦ እንዲያደርግ ያበረታታዋል እንላለን፡፡

ታላቁ የእግዚአብሔር ነብይ ነህምያ በመጽሐፉ በም.፪ ከቁ. ፳ “ የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፤ እኛም ንጹሓን ባሪያዎቹ ተነስተን እንሠራለን ” እንዲል፡፡
ይህን ታላቅ ሃገራዊ አጀንዳ ማን ይምራው?

ብፁዓን አባቶቻችን !
ምንም እንኳ የችግራችን መነሻና መድረሻ የየዘመናቱ የፖለቲካ አሰላለፎች በመሆናቸው መፍትሄውም ፖለቲካዊ ቢሆን እና ሂደቱንም ሃላፊነት ወስዶ የሚሳተፈውም ሆነ የሚያስተባብረው/የሚተባበረው ፖለቲካዊ የበላይነት የያዘው የወቅቱ አሸናፊው ቡድን ቢሆን ሂደቱን እጅግ ያቀለው ነበር (የታለቁን መሪ የማዲባን ሃገር እና የANCን ታላቅ አስተዋፅኦ ልብ ይሏል)፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ሰአት ኢህአዴግ በያዘው አቋም ይህን ታላቅ የእፎይታ መንገድ ለማግኘት የምንችል አልመሰለንም፡፡ በመሆኑም እነሆ ይህ አብይ አጀንዳ እስከ ዛሬ ድረስ ባለቤት ሊያገኝ ሳይችል ቀርቷል የሚል እምነት ይዘናል፡፡
ብፁዓን አባቶቻችን !

ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ ኢህአዴግ ሂደቱን ካልተቀላቀለውና ካልመራው ተብሎ በይደር የሚቆይና በጊዜ መራዘም ብቻ ችግሩ የሚወገድ ያለመሆኑ ጉዳይ ነው፡፡ ይልቁንም ጊዜ በሰጠንና በተዘናጋን ቁጥር ይህ የደም ውርስ በፍጥነት እየተንከባለለ እኛ ዘመን ላይ እንደደረሰብን ሁሉ ወደቀጣይ ትውልዶች በቀላሉ እንዲተላለፍ ምቹ ሁኔታን እያመቻቸን የምንገኝ ይመስለናል፡፡ ስለሆነም ይህ ዘግናኝ የመጠፋፋት ሂደት ወደ ቀጣዮቹ ዘመናት ከመተላለፉ በፊት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት እንዲያገኝና ዳግመኛ እንዳይመለስ ሆኖ እንዲሸኝ ያሻል፡፡ ስለዚህ ይህን ሃገራዊ ሸክም ሊሸከምልን በሚችል አካል አማካኝነት ይህ ታላቅ ሃገራዊና ትውልዳዊ የመፍትሄ ጎዳና በጊዜ አንድ ቦታ ላይ መጀመር እንዳለበት ፅኑ እምነት ይዘናል፡፡
በመሆኑም ይህንንም ሂደት ሃላፊነት ወስዶ ለመምራት ለማስተባበር ከህዝቦቿ ጋር በስደት ከምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንና ከቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የተሻለ አንዳች አካል ያለ አይመስለንም፡፡ ይህንንም ለማለት ያስደፈሩንን ብዙ ምክንያቶቻችንን ማቅረብ በወደድን ነበር፡፡ ነገር ግን የእናንተን የብፁዓን አባቶቻችን ጊዜ መሻማትና በከንቱ ማድከም እንዳይሆን በማሰብ ለአብነት ያህል አንዷን ብቻ እናቅርብ፡፡ ይኃውም እናንተ ማለት ለእኛ ፡-

ከሁሉ አስቀድሞ ከመረጣችሁ፡ ከለያችሁና፣ በቀደሙት አባቶቻችን እግር ካስቀመጣችሁ በሃያሉ በእግዚአብሔር አብ ፀጋ፣ ቅድስት ቤተክርስቲያኑን በከበረ ደሙ በዋጃትና በመሠረታት በቅዱሱ በእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር ፣ እናንተም ዘወትር በመካከላችሁ ሆኖ በሚያፅናናችሁና በሚያፀናችሁ በቅዱሱ የእግዚአብሔር መንፈስ በመመራት ስለ ፍቅር፣ ሠላምና፣ አንድነት በመትጋት መንጋውን ከክፉው ሁሉ የምትጠብቁ መልካም እረኛዎቻችን እንደሆናችሁ እናምናለን፡፡
ቅዱስ ዩሐንስ በወንጌል በም. ፳፩ ከቁ. ፲፭ -፲፰ “. . . ጴጥሮስም ሶስትጊዜ ትወደኛለህን? ስላለው ተከዘ፤ “ጌታዬ ሆይ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እኔም እንደምወድህ አንተ ታውቃለህ” አለው፤ “እንኪያስ ግልገሎቼን ጠብቅ” አለው . . . ” ብሎ እንደ መሰከረው፡፡

ሂደቱ እንዴት ሊተገበር ይችላል?
ብፁዓን አባቶቻችን !

እንግዲህ የእኛ ተማፅኖ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን እና ቅዱስ ሲኖዶሱ እንደ ተቋም ሃላፊነቱን ወስዳችሁ ሂደቱን እንድትመሩ እንጂ ከዚህ በዘለለ መልኩ በዝርዝር ጉዳዮችና አፈፃፀሙ ላይ ሃሳብ ለማቅረብ አይደለም፡፡ ይህም ከእውቀትና ከልምድ ማነስ የተነሳ ነው፡፡ ይልቁንም ኢትዮጵያ ሃገራችን የሊቃውንትና የደጋግ ልጆች ደሃ አይደለችምና አጠቃላይ ሃላፊነቱን ቅዱስ ሲኖዶሱ በመውሰድ፤ የሚመራውና የሚቆጣጠረው አንድ አካል በመሰየም በመላው አለም እንደ ጨው ዘር ተበትነው የሚገኙ ታዛዥ ልጆቻችሁን በማስተባበርና ቡራኬ በመስጠት ይህንን ታሪካዊና ትውልዳዊ መርገም በተሰጣችሁ ፀጋ እግዚአብሔር በመታገዝ በፍቅርና በይቅርታ ታፀዱልን ዘንድ በሃያሉ በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ተማፅኗችንን እናቀርባለን፡፡
በዚሁ አጋጣሚም መላው ወገናችን ለዚህ ታላቅ የይቅርታ ህይወት እራሱን ከወዲሁ እያዘጋጀ፣ የብፁዓን አባቶቹን የፍቅር፣ የሰላምና፣ የእርቅ ጥሪ በንቃት እንዲጠባበቅና፣ ለስኬታማነቱም ተግቶ እንዲታዘዝ እና እንዲረባረብ ወገናዊ ጥሪያችንን ከታላቅ አክብሮት ጋር እናቀርባለን፡፡

በመጨረሻም ነገራችን ሁሉ ያለዕውቀትና ማስተዋል የተዘበዘበ “ልጅ ያቦካው” አይነት ነውና አንዳች እናንተንና ህዝባችንን የሚያሳዝንና የሚያስከፋ ነቀፋ ቢገኝብን ፍፁም የሆነው አባታዊ ይቅርታችሁ ከወዲሁ ይደረግልን ዘንድ የአማላጃችንና የእናታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ጣፋጭ ስም ጠርተን እጅ ነስተናል፡፡

ወስብሃት ለእግዚአብሔር

ልጆቻችሁ
ከሰሜን አሜሪካ – ጥቅምት ፳፻፯ ዓ.ም
ግልባጭ ፡-
ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ለብፁዕ አቡነ መልከፄዴቅ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ
ለብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በሙሉ (በየሃገረ ስብከታቸው)

Hiber Radio:ኢትዮጵያዊያኑ በዲሲ የኢሕአዴጉን አቃቤ ሕግ በተቃውሞ አንገት አስደፉ * በዱባይ በኢትዮጵያዊቷ ላይ የወሲብ ጥቃት የፈጸመው በነፃ ተለቀቀ

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ ጥቅምት 23 ቀን 2007 ፕሮግራም !

<...>

አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ የመኢአድ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ በአንድነት ላይ ሰሞኑን በገዢው ፓርቲ የተከፈተውን ዘመቻ አስመልክቶ ለህብር ሬዲዮ ከሰጠው ምላሽ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡ)

የጥቅምት 22 ቀን 1998 የዲሞክራሲ ሰማዕታት ልዩ ትውስታ(ልዩ ዝግጅት)

የቡርኪናፋሶ አብዮትና የዜጎች ህልም የወታደሩ ተመልሶ ስልታን መያዝ (ልዩ ዘገባ)

የኡበር አማራጭ የትራንስፖርት አገልግሎትና በቬጋስ የገጠመው ግብ ግብ ውይይት ከተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች በታክሲና ኡበር በአገልግሎት ላይ ካሉ ጋር የተደረገ ቆይታ (ውይይት ክፍል ሁለት )

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

በዲሲ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በአገር ቤት ጋዜጠኞችንና የተቃዋሚ አባላትን የሚከሰውን ዐቃቤ ሕግ አግኝተው አንገት አስደፉ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በጨለማ ከቅሊንጦ ወደ ዝዋይ እስር ቤት ተዛወረ

አምንስቲ ኢትዮጵያ ገብቼ የሰብዓዊ መብት ጥሰቱን እንዳላጣራ ተከለከልኩ አለ

እንግሊዝ ለኢህአዴግ ፖሊስ ማሰልጠኛ የምታደርገውን የ27 ሚሊዮን ፓውንድ የገንዘብ ድጋፍ አገደች

በዱባይ ኢትዮጵያዊቷ ላይ የወሲብ ጥቃት የፈጸመው በነጻ ተለቀቀ

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ አሜሪካን ጨምሮ ለህወሃት ኢህአዴግ አገዛዝ የገንዘብ ድጋፍ የሚሰጡ አገራትና ድርጅቶች ከጊዜያዊ ይልቅ ዘላቂ ጥቅማቸውን እዲያጤኑ አሳሰቡ

አንድነት ፓርቲ የጥቅምት 22 ሰማዕታትንና የሕሊና እስረኞችን በሻማ ማብራት ዘከረ

በዲሲ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የታክሲ አሽከርካሪዎች ኡበርን ተቃወሙ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

ቅ/ሲኖዶስ: በምዕራብ ወለጋ እና ቄለም ወለጋ የተሐድሶ መናፍቃን ፈተናና በጋምቤላ የጸጥታ ችግሮች ጉዳይ ውሳኔ አሳለፈ

$
0
0

ሐራ ዘተዋሕዶ

his-grace-abune-henok-archbishop-of-west-wollega-and-asossaበቅዱስ ሲኖዶስ የተወገዙ የተሐድሶ መናፍቃን (አላውያን) ድርጅቶችና ግለሰቦች አስተዳደራዊ ችግርንና ጎሳዊ ርእዮታዊ ጥላቻን ሰበብ በማድረግ ቤተ ክርስቲያናችንን ከሕዝቡ ነጥሎ ለማዳከም በኅቡእ እና በገሃድ የሚያራምዱትን የክሕደት ትምህርት ማጋለጥ ጠንካራ የጋራ መግባባትና አቋም ተይዞበታል፡፡

በምልመላና ቅበላ ክፍተት ሳቢያ ወደ ቤተ ክርስቲያናችን የትምህርት ተቋማት ሰርገው ገብተው እንጀራዋን እየበሉ ለፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አራማጅ ድርጅቶች እንደሚሠሩ የተጠረጠሩ ተቋማቱንና ብዙኃን ደቀ መዛሙርቱን የማይወክሉ ግለሰቦች ጉዳይ ተጣርቶ ለውሳኔ የሚቀርብበት አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡

ብፁዕ አቡነ ኄኖክ፤ የምዕራብ ወለጋና አሶሳ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ (ፎቶ: ናሽቪል ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት)

ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶን ‹‹የምኒልክ ሃይማኖት›› እያሉ የአንድ አካባቢ በማድረግ ሕዝቡን ለሚከፋፍሉ የተሐድሶ አላውያን ምላሽ የሚሰጥ እና ምእመኑን በእምነቱና በአንድነቱ የሚያጸና መጠነ ሰፊ ስምሪት ይካሔዳል፡፡

በአህጉረ ስብከቱ በጥቂት አባወራዎች የሚጠበቁ የገጠር አብያተ ክርስቲያንም የሚረዱበት፤ በምዕራብ ወለጋና አሶሳ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኄኖክ የሚመራ ሀገር አቀፍ ትብብር ይቋቋማል፤ ምእመኑን በቋንቋው የሚያስተምሩ ሰባክያነ ወንጌል ይመደባሉ፤መጻሕፍትና በራሪ ወረቀቶች ይዘጋጃሉ፡፡

ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ፤ የጋምቤላ እና ኢሉባቦር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

በጋምቤላ ካህናትና ማእመናን ለኅልፈተ ሕይወት በተዳረጉበትና በእርስ በርስ ግጭት ለተጎዱ ኹሉም ወገኖች ጸሎት የምታደርግበትንና የሰላም መልእክቷን የምታደርስበትን፤ ከኑሯቸው ለተፈናቀሉትም ድጋፍ የምታደርግበትን የማስተባበር ሥራ ትሠራለች፡፡

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>
<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596344.js" async> </script>