Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ተመስገን ደሳለኝ 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት

$
0
0

temesgen1የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በዛሬው ቀን በዋለው ችሎት 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት፡፡ ፍትህን ሲያሳትም የነበረውና ሁለተኛ ተከሳሽ የሆነው ማስተዋል ህትመትና ማስታወቂያ በ10 ሺህ ብር ቅጣት ተጥሎበታል፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጥቅም 3/2007 ዓ.ም የመንግስትን ስም ማጥፋት፣ ህዝብን ማነሳሳትና የህዝብን አመለካከት ማናወጽ በሚሉ ሶስት ክሶች ጥፋተኛ የተባለ ሲሆን አሁን የተፈረደበት በትኛው እንደሆነ ባይታወቅም በአንደኛው ክስ ነው ተብሏል፡፡ የጥፋነኝነት ክሱ በተነበበት ወቅት ግን ‹‹መንግስት ይገድላል፣ ያፍናል፣ ይጨቁናል ብሎ ጽፏል፡፡›› በሚል ጥፋተኝ ነው ተብሏል፡፡

አቃቢ ህግ የቅጣት ማክበጃ ያላቀረበ ሲሆን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝም ሆነ ጠበቃው የቅጣት ማቅለያ አላቀረቡም፡፡ በሌላ በኩል የጋዜጠኛው ጠበቃ አምሃ መኮንን ይግባኝ እንደሚጠይቁ አስታውቀዋል፡፡ (ምንጭ: ነገረ ኢትዮጵያ)


የአፋር ህዝብ እንደ ባህል የሚያየውን እጥቅ ለመንግስት እንዲያስረክብ ታዘዘ (የማሣሪያ ማስመዝገቢያውን ሰርተፊኬት ይዘናል)

$
0
0

አኩ ኢብን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው፦

ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ በአፋር ክልል እንደ አዲስ ህግ ህዝቡ የጦር መሳሪያውን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለመንግስት እንዲያስረክብ የሚል ህግ ወጥቷል። ይህን ትእዛዝ ብዙዎችን ያስቆጣ ሲሆን ህጉ የወጣው በሰሜን አፋር የአፋር ነዋሪዎችና የትግራይ ምልሻዎች ተጋጭው አንድ የአፋር ወጣት ከሞተበት ግጭት በኋላ ነበር።
afar gun
በ1998 ዓ.ም አቶ መለስ ዜናዊ በፓርላማ ላይ ስለ አፋር ህዝብ እጥቅ ተጠይቀው ሲመልሱ «የአፋር ህዝብ እጥቅ ባህልና ለእንስሳ ጥበቃ እንጂ ለሽብር አይደለም።» ብለው ነበር አሁንስ? ወደ ሽብር ተቀይሮ ይሁን? ብቻ አላውቅም ግን እንኳን ጠመንጃ ባለ ብዕርም አሸባሪ እየተባለ አይደለም እንዴ? በአሁን ወቅት እኮ የኢህአዴግ ቲፎዞ ካልሆንን አሸባሪ ወይም አሸባሪዎች የምንባልበት ጊዜ ላይ ነን።

እና ወደ መረጃው ስመልሳችሁ ይህን ትዕዛዝ ተከትለው አንዳንድ የአፋር ወጣቶች ከነመሳሪያቸው ጫካ ገብተዋል። ይህን ግን ለአፋር ህዝብ ቀላል ፍርድ አይምሰላችሁ የአፋር ህዝብ እስከ ዛሬ መብቱን የሚያስከበረው በእጁ ነው። ይህ ደግሞ ህወሃት ካለው እቅድ አንፃር ሲታይ ህወሃት ካቀደው ከጀቡቲ መቀሌ ለሚዘረጋው የባቡር ሐዲድ ዝርጋታና ካላቸው ብዙ የአፋር መሬቶች የማጠቃለል እቅድን በቀላሉ ለማሳካት ከሚደረጉት እንቅስቃሴዎች አንድ አካል ነው ብለን እናምናለን። ወያኔ ዳሉልን ጨምሮ በአፋር ክልል በማዕድን እና ጨው የሚታወቁ ቦታዎች ወደ ትግራይ ማጠቃለል ይፈልጋል። ስለዚህ ይህን ተግባራዊ ለማድረግ ካለቸው ስትራቴጂ አንዱ የአፋር ህዝብ የታጠቀውን መሳሪያ ለመንግስት እንዲያስረክብ ማድረግ ነው።

ሁለተኛው ደግሞ በአፋር ወሳኝ ቦታዎች ላይ የትግራይ ተወላጆች በሰፈራ ፐሮግራም መኖር ሲሆን ለሰፈራ ሲመጡ ለልማት ነው ተብለው የሚመጡ ሲሆን በመንግስት የመኖሪያ ቤቶች ይሰራላቸዋል። ካሁን በፊት 60 ሺ የትግራይ ተወላጆች በትንዳሆ ሱኳር ፈብሪካ ስም በአፋር ክልል በአይሳኢታ፣ በዱበብቲና በሚሌ መኖሪያ ቤታቸው ተቀብለው መኖር ጀምረዋል። እዛ አካባቢ ሲኖሩ የነበሩ የአፋር ነዋሪዎች በማይረባ ካሳና በግዴታ ተፈናቀሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የአብዴፓ መደበኛ ጉባኤ በሰመራ በሉሲ አደራሽ ተካሄደ፤

ባለፈው ቅዳሜ 15/2/ 2007 የተጀመረው ይህ ሰብሰባ ላይ የተለያዩ አጀንዳዎች የቀረቡ ሲሆን ይበልጥ ያተኮሩበት ለመጪው ምርጫ ስለሚወዳደሩ እጩዎች ነበር። ስብሰባውን ማዘጋጀት የነበረበት የክልሉ አቢይ ኮሚቴ ቢሆንም ባልታወቀ ምክንያት የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሰብሰባን እንዲመሩ ተደርጓል። በስብሰባው ላይ በሴኔጋል የሚገኘው የአፍሪካ አምሳደሮች ማህበር ሊቀመንበርና የአብዴፓ ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የሆኑት አምባሳደር ሃሳን አብዱልቃድር የተገኙ ሲሆን በአቶ እስማኤል አሊሲሮና በአምባሳደር ሀሳን መካከል አለማግባባት እንደተፈጠረ ምንጮችን ዘግበዋል። በመጨረሻም አብዴፓን ወክለው ለምርጫ የሚወዳደሩ እጩዎች የፓርቲውና የድርጅቱ ኃላፊዎች እንዲያቀርቡ ተወስኗል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአፋር ክልል የክልሉ መሪዎች እርስ በእርሳቸው ትልቅ አለመግባባት ውስጥ እንዳሉ ይነገራል። ለምሳሌ ፦ የፀጥታ ቢሮው አቶ ስዩም አወል እና የአቶ እስማዕል ሚስት ወ/ሮ ፋጡማ አብደላ አይነጋገሩም። የሸሪዓ ቢሮው ሃጂ እስማኤልና አቶ እስማኤል አሊሲሮ አይስማሙም። አቶ ስዩም አወል በክልሉ በክፍተኛ ማዕረግ ያላቸው የፖሊስ የልዩ ኃይልና የድህንነት ኃላፊዎች በእጃቸው ውስጥ ሲሆን ክልሉን እንደፈለጉ የሚያሸከርከሩ ባለስልጣን ናቸው። አሁን አሁን እነዚህ ባለስልጣናት ከመጪው ምርጫ በኋላ በነበሩበት ስልጣናቸው የመቆየት ዕዳላቸው የመነመነ ሆኖባቸዋል።

ምክንያቱም ኢህአዴግ በዚህ አራት አመታት ውስጥ ከአፋር ህዝብ ባጋጠመው ዘርፈ ብዙ ተቃውሞ ምክንያት የሆኑት በእነዚህ ባለስልጣናት ችግር በመሆኑ የህወሓት መሪዎች ተስፋ ቆርጠዋል። አቶ እስማኤል አሊሲሮን ጨምሮ እነዚህ ባለስልጣናት በየጊዜው «ከጫካ ተቃዋሚዎችን እናስገባለን» እያሉ የተወሰኑ ቤተሰቦቻቸውን ከጫካ የገቡ በማስመሰል ብዙ ሚሊዮን ብሮች ከኢህአዴግ የሚቀበሉ ቢሆንም የአፋር በረሃን ከኢህአዴግ ተቃዋሚዎች ነፃ ማድረግ አልቻሉም። ኢህአዴግ እንደሚያምነው ሁሉም በገንዘብ ሃይል አስተዳድራለሁ የሚለውን መርህ አብዴፓዎች ተግባራዊ ማድረግ አልቻሉም።

እንዲሁም በእስር ላይ የሚገኙ የኢትዮጵያን ሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የአፋርም ተወካዮች ከመሆናቸው አንፃር አሁንም በአፋር ህዝብ ውስጥ የኢህአዴግ አባል በጣም አነስተኛ ነው።

የ “ካዛንችሱ መንግስት በአዲሰ አበባ ማዘጋጃ ቤት” –ከግርማ ሰይፉ ማሩ

$
0
0

Girma Siefu
ዛሬ ጥቅምት 17/ 2007 እግር ጥሎኝ አዲሰ አበባ ማዘጋጃ ቤት ጎራ ብዬ ነበር፡፡ የታዘብኩት ነገር ያስታወኝ ኤርሚያስ ለገስ “የመለስ ትሩፋቶች” በሚል ባወጣው መፅሃፍ ውስጥ “የካዛንችስ መንግሰት” ብሎ ያስነበበንን በገሃድ ከካዛንችስ ቦታ ቀይሮ አዲስ አበባ መስተዳደር ግቢ ውስጥ መኖሩን ነው፡፡ የካዛንችሱ መንግሰት ምን እንደሚሰራ እዚህ መዘርዘር አይጠበቅብኝም፤ በጥቅሉ ግን የአዲስ አበባ ህዝብ “መርጦ” ወይም ቀጥሮ ያስቀመጣቸው ሰዎች ሳይሆን ውሳኔ የሚስጡት ሌሎች በስውር በደህንነት ስም በኢህአዴግ የተቀመጡ ሰውር እጆች መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
እነዚህ ሰውር እጆች ለእኛ ለተቃዋሚዎች አዲስ አይደሉም ለምሳሌ፤
· በሆቴሎች አዳራሽ ለማከራየት አንችልም ምንም ጠቃሚ ገንዘብ ቢሆን ሆቴሎች ፈቃደኞች አይደለም፤
· ማተሚያ ቤቶች የተቃዋሚ ፓርቲዎች ወይም እነርሱን ይደግፋሉ የሚባሉ የግል ጋዜጦችና መፅሄቶች አያትሙም፤
· መብራት ኃይል ለአንድነት የማተሚያ ማሽን ሊያንቀሳቅስ የሚችል የኤሌትሪክ ሀይል (ሰሪ ፌዝ የሚባል ሀይል) ለፓርቲ ለማስገባት ፈቃደኛ አይደለም፤
· ቤት አከራዮች ቤታቸውን ለማከራየት ይፈራሉ፤
· በቅስቀሳ ጊዜ መኪና እና የድምፅ መሳሪያዎች ማግኘት ፈተና ነው፤
· ለቅስቀሳ የወጡ ሰዎች እንደ በግ በየጣቢያው ሲታሰሩ የሚያስሩት ሰዎች በግልፅ ዩኒፎርም የለበሱት ፖሊሶች ሳይሆኑ በሬዲዮ የሚያዙ ማን እንደሆኑ የማይታወቁ ናቸው፤ ወዘተ

ይህ ሁሉ የሚሆነው በህግ አግባብ ሳይሆን በሰውር መንግስት ውስጥ ያሉ ሰውር እጆች የሚሰሩት ነው፡፡
ለዛሬ ፅሁፌ መነሻ የሆነኝ ግን በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የህዝባዊ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ኦፌሰር የሆኑት አቶ ማርቆስ ብዙነህ የሰጡን ምላሽ ነው፡፡ አንድነት ፓርቲ በቀጣይ ፓርቲው በሚያደርገው እንቅስቃሴዎች የፓርቲ አባላትን በስነ ምግባር የታነፁ እና ሰላማዊ ትግል በሰለጠነ መንገድ የሚደረግና በግብግብ ሳይሆን በሃሳብ የበላይነት የተመሰረተ እንዲሆን ለማድረግ ለሚያካሂደው ስልጠና ለማካሄድ አዳራሽ ለመከራየት ባቀረብነው ጥያቄ በጎ ምላሽ እንደሌለ ከውስጥ ሰምተን ምክንያቱን በግንባር ለማወቅ ሄጄ የሰማሁት ምላሽ በአንድ መንግሰታዊ ተቋም ውስጥ ተቀጥሮ ደሞዝ ከሚበላ ሲቪል ሰራተኛ የሚጠበቅ ሆኖ አላገኘሁትም፡፡ የሰጡን ምላሽ “አራት ሰዎች መጥተው ፍቃዱ እንዳይስጥ ጠይቀው አለቃይ እንዳትሰጥ ስለአለኝ ነው የሚል ነው፡፡” በቃ ይህ ነው ምክንያቱ፡፡ አንድነት ፓርቲ ይህን ፈቃዳ ላለማግኘት አንድም ያጎደለው መስፈርት የለም፡፡ አቶ ማርቆስ አለቃቸው ይህን መልስ ሲሰጣቸው ለምን? እንዴት ብዬ? ከመመሪያ አንጻር ልክ አይደለም ብለው አይጠይቁም፡፡ አለቃቸውንም አይሞግቱም፡፡ እርሳቸውም የሚያውቁት አለቃቸውም ቢሆን እራሳቸው እንደማይወስኑ፡፡ የሚወስነው ይህ ስውር እጅ ያለው ካዛንችስ የነበረው አሁን በመስተዳድር ቅፅር ግቢ የሚገኘው መንግሰት እንደሆነ፡፡
አንድ መስሪያ ቤት ሰራውን የሚሰራው በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን በደንብ እና መመሪያ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ኦፊሰሮች ተግባራቸውን ሲያከናውኑ ደግሞ እነዚህ የህግ ማዕቀፎች መሰረት አድረገው ነው ብለን እንጠብቃለን፡፡ በዚህች ምስኪን ሀገር ግን ይህ ምፀት ነው፡፡ በህግ ማዕቀፍ የሚሰራ ኦፊስር ማግኘት ዘበት እየሆነ መጥቶዋል፡፡ አለቃው በቃል አድርግ ያለውን የሚያደርግ የማርቆስ ዓይነት ኦፊሰር ሞልቶ ተርፎዋል፡፡ በጣም የሚገርመኝ የዚህ ዓይነት ኦፊሰሮች ለልጆቻቸው ሰራ ሄጃላሁ የሚሉ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ባይሉዋቸው ደግ ነው፡፡ ይህን ሊያደርጉ መሄዳቸውን ሲያውቁ ያፍሩባቸዋል ብዬ ስለማስብ ነው፡፡ ለምን ለልጆቻችን ማፈሪያ እንደምንሆን አይገባኝም፡፡
መልካም አስተዳደር አስፍናለሁ የሚል መንግሰት መልካም አሰተዳደር የሚሰፍነው በአዳራሽ ኮፍያና ቲ ሸርት ለብሶ በሚደረግ ዲስኩር እንዳልሆነ የገባው አይመስለም፡፡ መልካም አስተዳደር የሚሰፍነው በህግ ማዕቀፍ አገልግሎት የሚሰጥ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኛ አገልግሎት ሲሰጥ እንጂ በስውር በቃል በሚሰጥ ትዕዛዝ እንዳለሆነ መረዳት ይኖርብናል፡፡ ማርቆስ በሚሰጠው መልስ እየተበሳጨ፣ እያዘነ ሲከፋውም እየተሳደበ የሚሄድ ተገልጋይ መዘዝ እንደሚያመጠ ግን የገባቸው አይመስለኝም፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው ደግሞ በስውር መንግሰት በዚህ መንገድ እንዲሆን ስለሚፈልግ ነው፡፡
ዛሬ በግልፅ የተረዳሁት በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ብሎም በሀገር አቀፍ ደረጃ መልካም አስተዳደር የማሰፈን ችግር ምንጭ በደህንነት ስም በስውር ያለው መንግሰት የሚሰጠው ትዕዛዝ ሲሆን፣ ሲቀጥልም አድርግ ያሉትን ለማድረግ በተጠንቀቅ ዝግጁ የሆነው የማርቆስ ዓይነት ደሞዝ እየበሉ ያሉ ሲቪል ሰራተኞች ናቸው፡፡ አለቃዬ እንዲህ አድርግ ብሎኝ ነው በሚል መመሪያን መሰረት ያላደረግ ትዕዛዝ የሚሰፈፅሙ የማርቆስ ዓይነት ኦፊሰሮች የዚህች ሀገር መከራ እንዲረዝም፣ ህዝቡ የመልካም አስተዳደር ትሩፋት እንዳያገኝ ተባባሪ እንደሆኑ አበክረን መንገር ይኖርብናል፡፡ ይህንን አሜን ብሎ የተቀበለ ህዝብ መከራውና ግፉ ተስማምቶኛል እንዳለ ይቆጠራል፡፡ የዚህ ዓይነት ህዝብ ደግሞ ምንም ዓይነት አንባገነን መንግስት ቢመጣ የሚገባው ነው ማለት ተገቢ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ኢህአዴግ አይመጥነንም ያለ ህዝብ በቃ!!!! ሊለው ይገባል፡፡ ኢህአዴግ በቃ ሊባል ይገባል!!!!

ቸር ይግጠምን

የማለዳ ወግ…. የተመስገን ደሳለኝ እናት…

$
0
0

የማለዳ ወግ … ይድረስ ለወዳጀ ወንድም ለወዳጀ ታሪኩ ደሳለኝ !

ወንድሜ ሆይ ማምሻውን ” … አሁን የማወራው ስለ ብትቱው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሳይሆን ስለ ሆደ ባሻዋ እና ርህሩዋ እናታችን ነው! ” በማለት ስለ እናትህ ጭንቀት የጻፍከውን ሳነበው ፣ ስለ እናትህ ልቤ በሃዘን ተጎዳ ፣ ስለ ጀግኖች ሳይሆን ስለ ጀግና እናቶች መከራ አነባሁ ፣ እንደ ሰው በእልህ ሰውነቴ ጋለ ፣ ተናደድኩ …በቁጭት ግን አልቆዘምኩም …!
yetemesgen enat
ምን እንደምል አላውቅም … ለተጎዱት እናታችን አዝናለሁ ፣ ብቻ ሳይሆን ለመስዋዕትነት ለቀረቡት ለዚህች ቁርጥ ቀን ግንባራቸውን እንደ ተሜ ለሰጡት ብርቱ የሃገሬ ልጆች እናቶች በሙሉ አዝናለሁ “..ልጅሽ ወንድሜ ታስሯል! ” ለምትለው የመርዶ ነጋሪው ያንተ ጭንቀት ቢገባኝም ወጣት ነህና እንባህን ጠራርገህ ወንድምህ የሰጠንን ቃል አክብር ፣ ተከተልም! የጀግና ዘር አያለቅስም ! ተሜ አልነገረህም ? ወንድ ልጅ አደኮ አያነባም … በቃ እንዲያ ነው !!!!

አንድ ወዳጀ ማምሻው ላይ ጋዜጠኛ ተመስገንን ታውቀዋለህ? አለኝ … እንዲህ መለስኩለት ወዳጀ Abdu ጋዜጠኛ ተመስገንን በአካል አውቀዋለሁ፣ ከሳውዲ ለእረፍት ሄጀ በአንድ መአድ ቁጭ ብለን ክፉ ደጉን አውርተናል። ከርሴን ልሞላ የተሰደድኩትና “በካሳደገኝ ላስተማረኝ ወገኔ አልለይም ፣ ከምወዳት ኢትዮጵያ ፣ አልሰደድም እንቢ ” ካለው ጋዜጠኛ ጋር የነበረን ቆይታችን ያማረ ነበር። ተሜ ከሃገር ውስጥ ፖለቲካ፣ ማህበራዊ ኑሮውና ከዚያም አልፎ በሳውዲ በምንኖር ኢትዮጵያውያን ጥልቅ ግንዛቤ ያለው ወንድም መሆኑን ባውቅም ያኔ ደግሜ አረጋግጫለሁ። በኢትዮጵያ ላይ የመጣው አበሳ እያዘነ እየተቆረቆረ እንደ ዜጋና እንደ ባለሙያ ራዕዩን ሲያንሸራሽር የደረሰበት እንግልት ግድ የማይሰጠው ጀግና ወጣት ጋዜጠኛ ነው። እንዲያው በአጠቃላይ እኔ ኢትዮጵያን እወዳታለሁ ማለት ይቀል ይሆናል ፣ ኢትዮጵያን እንደ ተሜ እወዳታለሁ ማለት አይቻልም። እሱን መሆን የእሳይ ወላፈኑን ፣ ረመጥ እሳቱን ጭምር እየተለበለቡ ኢትዮጵያን መውደድ ከቶ ማንስ ይቻለዋል። ለብዙዎቻችን በጣም በጣም ከባድ ነው ! በቆይታችንና ከተሜ ጋር ባለን ቀረቤታ የተረዳሁት ይህን እውነታ ነው! ስለ ኢትዮጵያና ስለህዝቧ ራዕዮን ስድብ ፣ግልምጫ ማግለሉ፣ ከመቶ ያለፈ ክሱ ፣ እስራት ፣ ፕሮፖጋንዳ ዘመቻው ምኑ ቅጡ ይህን ሁሉ ተጋፍጦ ጋዜጣ መጽሔቱን ሲዘጉበት እየከፈተ ” ትግሌ እስከቀራንዮ ነው ፣ አልሰደድም” ያለ እንደ ተሜ ብርቱ ጋዜጠኛ መች አለ ? ይህን ተሜ አውቀዋለሁ! የጀግና ቤቱ ወህኒ ነው እንዲሉ ፣ ተሜ ወደ ቤቱ ገብቷል ! በቃ ተሜ “ስለተገፋሁበት ምክንያት ስለኢትዮጵያ ትንሳኤ ትጉ እንጅ ስለእኔ እንዳታለቀረሱ ” ብሎኛል ተሜ …የማውቀው ብርቱው ወዳጀ ጋዜጠኛ ተመስገን …ብየ መለስኩ !

እናም እውነቴን ነው የምልህ ፣ በተሜ ኩራት የደም ስጋ ፣ የአንድ ማህጸን የእማማ ልጅ ስለሆንክ ክብር ይሰማህ እንጅ ተሜ ” አታልቅሱ ” ብሏልና አታልቅስ …ጋዜጠኛ ተመስገን ወደ ቀራንዮ በግርማ በክብር እየሄደ ነው ፣ ሆዳችን አታባባው … ዳሩ ግና ምን የሚባባ ሆድ አለን ? …
ብቻ ይሁን :(

ነቢዩ ሲራክ

“አቦይ ስብሐት ጎበዝ ነኽ አለኝ”ያሉት ፓትርያርኩ ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ተፋጠው ዋሉ

$
0
0

abune-matyas

አቶ አባይ ጸሐዬ ፓትርያርኩን ጎበዝ አለ

አቶ አባይ ጸሐዬ ፓትርያርኩን ጎበዝ አለ


የሐራ ተዋሕዶ ዘገባ፦

ፓትርያርኩ የማኅበራት ገንዘብ ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ገቢ ኾኖ በማእከል ካልተመራ በሚል ከማኅበራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ጋራ የሚቃረን ግትር አቋም ይዘው ውለዋል፡፡

አቋማቸው ተቀባይነት ካላገኘ ስብሰባውን ለመምራት እንደሚቸገሩ በመግለጽ ምልአተ ጉባኤን ለማስገደድ ያደረጉት ሙከራ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ጽኑ አቋም ሳቢያ አልተሳካላቸውም፡፡

ጉዳዩ ‹‹ከአዲስ አበባ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ጋራ ብዙ የሠራኹበትና የደከምኩበት ነው፤ በቀላሉ የምተወው አይደለም›› በሚል ከአክራሪነት ጋራ የተገናኘ ጽሑፍ ሲያነቡ ውለዋል፡፡

ከተጀመረ ስድስተኛ ቀኑን ያስቆጠረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የመጀመሪያ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ በዛሬ፣ ጥቅምት ፲፯ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. ሙሉ ቀን ውሎው፣ የ፲፱፻፺፩ ዓ.ም. ሕገ ቤተ ክርስቲያን ለማሻሻል በቀረበውና የልዩነት አቋም በተያዘባቸው የረቂቁ አንቀጾች ላይ ጠንካራ ውይይት ሲያደርግ አምሽቷል፡፡

የማሻሻያ ረቂቁ፣ ባለፈው ዓመት ግንቦት የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ኹለተኛ ዓመታዊ መደበኛ ስብስባ ወቅት አንቀጽ በአንቀጽ ከተወያየበት በኋላ ተጨማሪ እርማትና ማስተካከያ አድርጎ ለአኹኑ ምልአተ ጉባኤ እንዲያደርስ የሠየመው ስድስት አባላት ያሉት የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሊቃውንትና የምሁራን ኮሚቴ ያቀረበው ነው፡፡

የማሻሻያ ረቂቁንና በኮሚቴው አባላት መካከል የልዩነት አቋም የተያዘበትን ቃለ ጉባኤ ባለፈው ቅዳሜ ከቀትር በፊት ውሎው የተናበበው ምልአተ ጉባኤው፣ ለዛሬ በቀጠረው መሠረት ነው ፍጥጫ የተቀላቀለበት ውይይት ሲያደርግ የዋለው፡፡

የልዩነት አቋሞች የተያዘባቸው ነጥቦች፡-

የሊቃነ ጳጳሳትን ተጠሪነት(ዝውውር እና ምደባ)
የማኅበራትን ተጠሪነትና የገንዘብ እንቅሰቃሴ ማእከላዊነት
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አመራር የተመለከቱት ይገኙበታል፡፡
ከስድስት የኮሚቴው አባላት መካከል በሦስቱም ነጥቦች ላይ የልዩነት አቋማቸውን በቃለ ጉባኤው ያስመዘገቡት የፓትርያርኩ ልዩ ጸሐፊ ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ ናቸው፡፡ ልዩ ጸሐፊው ከአምስቱ የኮሚቴው አባላት ተለይተው በያዙት አቋም÷ የሊቃነ ጳጳሳቱንና የማኅበራትን ተጠሪነትን ለቅዱስ ሲኖዶስ የሚያደርጉት የረቂቁ አንቀጾች ለፓትርያርኩ ይኹን በሚል እንዲተኩ፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትም የፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት እንደኾነ የሚገልጽ በረቂቁ ያልነበረ አንቀጽ በግልጽ እንዲቀመጥ ተከራክረዋል፡፡

ስለ አቶ መለስ ዜናዊ ቀበቶ ያወራችው ዘፋኝ ሃይማኖቷን ቀየረች

$
0
0

weyso
(ዘ-ሐበሻ) አቶ መለስ ዜናዊ የሞቱ ሰሞን በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ቀርባ “አቶ መለስ ቀበቶ እንኳ አድርገው አያውቁም ነበር” በሚል ተናግራ በብዙዎች ትችት ውስጥ ወድቃ የነበእረችው ዘፋኝ ትዕግስት ወይሶ ኃይማኖቷን ቀየረች።

“ቆጨኝ” በሚል ዘፈኗ የምትታወቀውና በተለይም ስለአቶ መለስ ቀበቶ በመናገር ታዋቂነትን ያተረፈችው ትዕግስት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖቷን ቀይራ የፕሮቴስታንት ኃይማኖት ተከታይ መሆኗን አስታውቃለች። ት ዕግስት አቶ መለስ በሞቱ ሰሞን ካልጠፋ ምሳሌ ዘላ ቀበቷቸው ላይ ማተኮሯ የብዙዎች መነጋገሪያ አድርጓት እንደነበር ይታወሳል።

“ሕይወቴን ለእየሱስ ሰጥቻለሁ” ስትል ለኤፍታህ ኃይማኖታዊ መጽሔት ቃለምልልሷን የሰጠችው ትዕግስት ወይሶ ሙዚቃ ማቆሟን እና ወደ መዝሙር እንደምትገባ አስታውቃለች።

ቦሌ ከወሎ ሰፈር እስከ ደንበል ህንፃ በወረቀት መፈክሮች አሸብርቆ አደረ

$
0
0

etv propaganda 1

etv propaganda tikur shiber

etv propaganda

ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 18/2007 ከቦሌ ወሎ ሠፈር እስከ ደምበል ህንፃ ድረስ በወረቀት ላይ በተፃፉ መፈክሮች አሸብርቆ ማደሩን ቢቢኤን ራድዮ ዘገበ።
እንደራድዮው ዘገባ ከሆነ መብት መጠየቅ ሽብር አይደለም ፣ በመንግስታዊ ጥቁር ሽብር ተስፋ አንቆርጥም ፣ ትግላችን እስከ ድል ደጃፍ ይቀጥላል በሚሉ መፈክሮች በየቦታው ተለጥፈው ማደራቸው ታውቋል።

ሙስሊሙ ማህበረሰብ የጠየቀው ሰላማዊ ጥያቄ እስኪመለስ ተቃውሞውን በሰላማዊ መንገድ እየገለፀ ይገኛል።

ልማት ካለ ነፃነትና ፍትሕ ፋይዳ የለውም –ክፍል ሁለት

$
0
0

ከ ይኩኖ መስፍን

ቦስተን ሰሜን አሜሪካ

መልካም አስተዳደርና የፓለቲካ ምሕዳር

Justiceየሞያ ነፃነት በተገደበባት” ነፃ የፍትሕ” የዳኝነትና የዴሞክራሲ ተቋማት በሌሉበት! የሕግ የበላይነትና ተጠያቂነት በጠፋበት” በጋብቻና በዝምድና የተሳሰረ አንድ ፈላጭ ቆራጭ ፓርቲ የሀገሪትዋን ሁለንትናዊ ሰብኣዊ ማተሪያላዊና አእምራዊ ሀብት ተቆጣጥሮ ራሱ ሕግ አውጪ! ራሱ ሕግ ተርጓሚ! ራሱ ሕግ ፈፃሚና አስፈፃሚ በሆነበት” ባጠቃላይ ፍርሃት! ዱላ! ድሕነትንና ረሃብን እንደ የፓለቲካ መሳሪያ አድርጎ በመጠቀም ለያይቶና አደንቁሮ የሚገዛ አምባ ገነን መንግስት ባለበት ድሃ ሀገር የሚኖር ሕብረተሰብ ምን ያህል ለአፈና! አድልዎ! ጭቆና እና ዝርፊያ የተጋለጠ እንደሆነ መገመቱ አያዳግትም::

አብዛኞቻችን ከደርግ ውድቀት በሗላ በእርስ በርስ ጦርነት የደቀቀውን ሀገርና ህዝብ እፎይታ አግኝቶ በይቅርታ መንፈስ ሁላችንም በአንዲት እናት ሀገር ጥላ ስር ታቅፈን! ተቻችለን! ተፋቅረንና ተከባብረን በጋራ የምንገነባት አንዲት ዲሞክራሲያዊት እናት ሀገር ትኖራለች የሚል ነበር ተስፋችንና ምኞታችን፡፡ የህወሓት/ኢሕአዴግ ስርዓትም ካለፉት መንግስታት ተምሮ በሀገራችን ቢያንስ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት መሰረት ይጥል ይሆናል የሚል በጎ እምነትና ግምት ነበረን፡፡ በሂደት የሚታዩ አንዳንድ የልማት እንቅስቃሴዎችም እንደ መልካም ጅምር በመውሰድ” ነገር ግን በመልካም አስተዳድር! በፓለቲካዊ ምሕዳር! በምርጫና በሀገራችን ድሕንነት ዙሪያ የሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዛሬ ነገ ይታረማሉ በማለት ዜጎች በተደራጀም ሆነ በተናጠል ላለፉት አሰርቱ ዓመታት ብሶታቸውን ሲያሰሙና አቤት ሲሉ ቆይቷል:: ይሁን እንጂ ሰሚ ጆሮ አልተገኘም::

ህወሓት/ኢሕአዴግ በትረ ስልጣኑን ከጨበጠና ካደላደለ በሗላ እሱም በተራው የጥፋት መንገድ በመከተል የህዝቡን የለውጥ ጥማትና የፍትሕ ተስፋ አጨልሞታል:: ትናንት በደርግ ቀይ ሽብር የተቀጣውና የደነገጠው ሕብረተሰብ ለውጥ ይመጣል ብሎ ሲጠብቅ ዛሬም በፀረ ሽብር አዋጅ እንዲገዛ! እንዲሸማቀቅና እንዲሰጋ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ትላንት ለዴሞክራሲና ለሰው ልጅ ነፃነት ሲባል የተከፈለውን ኩቡር የህይወት መስዋእትነት ተረስቶ ዛሬ የህወሓት/ኢሕአዴግ የአንድ ድርጅት አባልና ታማኝ ካልሆንክ በስተቀር የመደራጀት! የመናገር! የመስራት! ባጠቃላይ እንደ አንድ ዜጋ በህይወት የመኖር ነፃነትህን ተነጥቆ ለፍልሰት! ለእስር! አሊያም ለሞት ትዳረጋለህ፡፡ የተከበረና አኩሪ ባህል ያለው ጨዋ ህዝብ ዛሬ ወዳጅ” ማሀል ሰፋሪና ጠላት ብሎው በመፈረጅና በመከፋፈል አንዱ አንዱን የገዛ ወንድሙን በጎሪጥና በጥርጣሬ ዓይን እንዲተያዩ እየተደረገ ይገኛል፡፡ አንድ ዜጋ የተለየ ሃሳብ ወይም የሌላ ድርጅት አባል በመሆኑ ብቻ እንደ ነውርና እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ በህዝብ ፊት የተለያዩ አስነዋሪ የማስፈራሪያ ዘዴዎችን እየተጠቀሙ በተወለባት ምድር ሓፍረት እንዲሰማው” ከሕብረተሰቡ እንዲነጠልና እንዲሰጋ ከማድረግ ባሻገር ይባስ ብለው ሲሞት እንዳንቀበረው” እሳት እንዳናስጭረው” የሚል የወረደ ማሕበራዊ ውግዘትና ተፅእኖ እንዲፈፀምባቸዉ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ሌሎችም በዚሁ ፅሑፍ ለመጥቀሱ የሚከብድና የሚዘገንን ድርጊት በተለይም ለአርባ ዓመታት ያህል በአንድ ሞኖፓላዊ ድርጅት ህወሓት ተይዞ የሚገኘው የትግራይ ህዝብ ታሪኩንና መለያ ባህሉን (Indeginous culture) በጉልበት በማፈራረስ እና በመበረዝ በምትኩ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ቅይጥና የተዳቀለ የካድሬዎች ግራ አስተሳሰብ እንዲተካ በማድረግ እርስ በርሱ እያናከሱ በላዩ ላይ ይህ ነው የማይባል ግፍ እየተፈፀመበት ይገኛል፡፡

ልብ በሉ!! ተወልደን ባደግንበትና እትብታችንን በተቀበረበት መንደር ዛሬ ይህ ዓይነት የስነ ልቦና ጦርነት በያንዳንዳችን ቤት ቢደርስብን ምን ይሰማናል? ትላንት ጫካ ገብተው ስለ ነፃነት ሲዘምሩ! በሰማእታት ስም ሲምሉ! ለህዝብ ሲያስተምሩና በሽዎች የሚቆጠሩ ለጋ ወጣቶችን ቀብረው ስልጣን ላይ የወጡ የፓለቲካ መሪዎቹ ያ ሁሉ ለህዝብ የገቡበትን ቃል ረስተው ዛሬ ብዙሃኑን ለልመናና ለስቃይ ዳርገው እነሱ በሙሱና ሲጨማለቁ! ከሕግ በላይ በመሆን በህዝብ መብት ላይ ሲቀልዱ! በገዛ ወገናቸው ላይ ሲጨክኑና ሲያሰቃዩ በውል ስናይ እውነት ምን ይሰማናል? የህወሓት/ኢሕአዴግ ስርዓት የሁሉም ዜጋ ሕገ መንግስታዊ መብትና ደሕንነት ጠብቆ በእኩል ከማስተዳደር! ከመጠበቅና እንደ መንግስት ከመስራት ይልቅ ራሱን ታች ወርዶ ከሕብረተሰቡ ወይም ተቃዋሚ ናቸው ከሚላቸው ሰዎች ጋር የሚናቆርና የሚያውክ ከሆነ ህዝቡ ለማን አቤት ይበል?

ዛሬ የምንኖረው በ21ኛው ክፍለ ዘመን የሰው ልጅ ከአካባቢው የእይታ አድማስ አልፎ ዓለምን መዳሰስ በጀመረበት” በተለይም ዴሞክራሲ” የሕግ የበላይነት” መልካም አስተዳደር” ሰብኣዊ መብትና የነፃነት ጥያቄዎች ድንበር አልባ (ዩኒቨርሳል) የሰብኣዊ ፍጡር እሴቶች በሆኑበት በሰለጠነ ዘመን ሆኖ ሳለ ነገር ግን ህዝባችን ብሎም ወጣቱ ትውልድ አደንቁረህ ግዛ በሚል የህወሓት/ኢሕአዴግ ያረጀ ያፈጀ ፈሊጥ ሳይወድ በግድ እንደ ወባ ክትባት የአንድ ፓለቲካዊ ቡድን ጠባብና ሞኖፓላዊ አስተሳሰብ ተሸብቦ እንዲያድግ የሚገደድበት ምክንያት ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎች ለሰሚ ብቻ ሳይሆን ለተመልካችም ግራ የሚያጋቡ የዘመናችን የሀገራችን እንቆቁልሽ ናቸው፡፡

የተከበራችሁ ውድ ኢትዮ}ያውያን ወገኖቼ ሆይ!!

በሀገር ቤት ቆይታዬ እስካሁን ድረስ በአእምሮዬ ውስጥ እየተመላለሱ የሚረብሹኝ ብዙ ነገሮችን ታዝቤያለሁ፡፡ ሁሉም ያየሁትንና የሰማሁትን የህዝቡን እሮሮ በዚህ አጭር ፅሑፍ ዘርዝሮ ለማቅረብ የሚከብድ ቢሆንም ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜኑ ክፍለ ሀገራችን በተለይም አርባ ዓመታት ያህል በአንድ ነፃ አውጪ ነኝ የሚል ፓለቲካዊ ድርጅት በህወሓት ሞኖፓላዊ አገዛዝ ወድቃ በአካባቢው ነዋሪዎች አጠራር የፓሊስ ግዛት (police state) እየተባለ የሚነገርላት ትግራይ ለወራት ያህል በቆየሁበት ጊዜ ያጋጠሙኝን አስደማሚና አስነዋሪ ነገሮችን ቢያንስ ሕብረተሰቡ ማወቅ አለበት ብዬ በማስታወሻዬ ዘግቤ ከያዝኩዋቸው አንዳንድ ነጥቦች ውስጥ ጥቂቶቹን ቆንጠር አድርጌ ላካፍላችሁ፡፡

ፍርሓት (ወኔ ሰላቢ በሽታ)

ህዝቡን አስደንግጦ! አስፈራርቶ! አሸብሮና ወኔ ሰልቦ መግዛት በደርግ ጊዜም የነበረ ቢሆንም የዛሬው ግን የረቀቀና ዓይን ያወጣ ሁኔታ ነው ያለው፡፡ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር የነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ለኢትዮ}ያ ህዝብ ካወረሱትና ካበረከቱት ትልቁ ስጦታና ራዕይ “ፍርሃት” ነው፡፡ ፍርሃት በአሁኑ ጊዜ ህወሓት/ኢሕአዴግ ህዝቡን አንበርክኮና ፀጥ ረጭ አድርጎ በሀይል ለመግዛት የሚጠቀምበት ትልቁ የፓለቲካ መሳሪያው መሆኑን እኔ ከምናገረው በላይ ነው፡፡ ፍርሃት በሕብረተሰቡ ውስጥ ገብቶ ምን ያህል አስከፊና አስፈሪ ሁኔታ እንደፈጠረ በይበልጥ የተረዳሁት ዘመድ ጥየቃ ከቦታ ወደ ቦታ ስንቀሳቀስ በደረስኩበት ቤት ሁሉ የማገኛቸው ሰዎች አንዳንዶቹ በስጋትና በጭንቀት ተውጠው እንባ እየተናነቃቸው ሲነግሩኝ ውስጤ በጣም ይሰማኝ ነበር፡፡ አዎ!! ሁኔታውን በአካል ተገኝቶ ለተመለከተው ሰው እውነትም ባለቤት ያጣ ያልታደለ ህዝብ! ያልታደለች ሚስኪንዋ ድሃ ሀገር! የሚያሰኝ ነው፡፡

ከዚህ በመነሳት ጥያቄ ለመሰንዘር ግድ ሆነብኝ፡፡ “እናንተ ዜጎች አይደላችሁም ወይ? በሀገሪቱ ሕግ የለም ወይ? ለመንግስት አቤት የማትሉበት ምክንያት ለምንድን ነው? የተሰማችሁ ሀሳብ ሁሉ ለሚመለከተው አካል በግልፅ ለመናገርና ለመቃወም ለምን ትፈራላችሁ?” ብዬ ብጠይቃቸው የሰጡኝ መልስ የሁሉም ሃሳብ ተመሳሳይ ነው፡፡ “እኛ የሕግ ዋስትና የለንም፡፡ መንግስትም ራሱ ለሕግ ተገኝ ካልሆነ ለማን አቤት ይባላል” የሚል ነው፡፡

“ስማ ወንድማችን! እኛን የሚያስተዳድሩን እኮ መንግስት የላካቸው ካድሬዎችና ታማኞች ናቸው፡፡ በሕብረተሰቡ ዘንድ አፍ ጠባቂዎች እየተባሉ የሚጠሩ የተለያዩ የስለላ መረቦች በየመንደሩ በውስጣችን እንዳሉ እናውቃለን፡፡ ለመቆጣጠር እንዲመቻቸውም ከላይ እስከ ታች ሕዝቡን አንድ ለአምስት አደራጅተውታል፡፡ ቀጥሎም የቤተ ሰብ ሸንጎ የሚባልም አለ፡፡ ከዚህም አልፎ የፌዴራል ፓሊስ! ያካባቢው ፓሊስ! ሚሊሻና የተለያዩ ስውር ታጣቂዎች ሁሉም በአብዛኛው ጊዜ የሚጠብቁት የህዝቡን ድህንነትና የዜጎች ህልውና ቅድሚ በመስጠት ሳይሆን የኛን ነፃ እንቅስቃሴ የሚገድቡና አፋችንን የሚጠብቁ ሀይሎችም ናቸው፡፡ ሌላ ቀርቶ በቤተሰብ መካከልም መተማመን የለም፡፡ ባል ካፈነገጠ በሚስቱ ወይም በዘመዶቹ ሚስት ካፈነገጠች ደግሞ በባልዋ ወይም በልጆችዋ እየገቡ ትዳር እንዲፈርስ ወይም እንዲካሰሱ ያደርጋሉ፡፡ ከተናገርክ ደግሞ አፍ እላፊ እየተባለ ከስራ ትባረራለህ! መሬትህን ወይንም ንብረትህን ትነጠቃለህ! በህዝብ ስም ከውጭ የሚመጣ እርዳታም እንዳታገኝ ይደረጋል! ከዚህም አልፎ እንደ ጠላት የተፈረጁ የተቃዋሚ ፓለቲካ ድርጅቶች ስም እየተለጠፈብህ የትምክህተኞች አቀንቃኝ! አሸባሪ ! ከሃዲ! ወዘተ በሚል ሰበብ ተከሰህ ወደ አቦይ ታአገስ (እስር ቤት) ትገባለህ፡፡ ከዚያ በሗላ ጠያቂ የለህም፡፡ ወይም ሀገር ለቀህ ትጠፋለህ አሊያም ትሰወራለህ፡፡ ባጠቃላይ ሌላ ሰው ወይም ሕብረተሰቡ ተቃውሞ ወይም የፍትሕ ጥያቄ እንዳያነሳ ለማድረግ እኔን አይተህ ተቀጣ የሚል ሌላ ስውር መልእክት በሚያስተላልፍ መልኩ ግፍ ይፈፀምብሃል፡፡

በዚህ ምክንያት የሆድ ቁስል ይዘን እያወቅን እንዳላወቅን አፋችንን ይዘን ዝም እንላለን፡፡ ለማንስ አቤት እንበል፡፡ ከጎጥ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ አመራር ያለው የካድሬና የስለላ ሰንሰለት ነው፡፡ እኛ እኮ በሀገሪቱ ሕገ መንግስት አለ ሲባል በወሬ እንሰማለን እንጂ ሕጉ ፈፅሞ እኛን አይመለከተንም፡፡ ሕግና ስርዓት ቢኖርማ እንዲህ አይሆንም ነበር፡፡ እኛ እኮ እስካሁን ድረስ የምንተዳደረው በትጥቅ ትግሉ ጊዜ ከነበረው የድርጅቱ ሕግና ስርዓት የተለየ አይደለም፡፡ ድሮ ሲያስተዳድሩን የነበሩት የህወሓት ካድሬዎች ናቸው አሁንም ከላይ እስከ ታች አፋችሁን ያዙ እያሉ እየኰረኰሙ እየገዙን ያሉት እነሱ ናቸው ሌላ አዲስ ነገር አልመጣም” እያሉ የነገሩኝ ብዙ ናቸው፡፡ በተለይም የቅርብ ዘመዶቼና ጓደኞቼ በጆሮዬ ሹክ እያሉ “ከሰው ጋር ብዙ አታውራ፡፡ ጠንቀቅ በል፡፡ ሲቪል መስለው ካድሬዎች ይከታተሉሃል፡፡” በማለት ምክር ይለግሱልኝ ስለነበር ከሌላ ሰው ቀርቶ ከቅርብ ዘመዶቼ እንኳን ሳይቀር ነፃ ሆኖ ለማውራት በጣም ከባድ ነበር፡፡

የሃሳብ ነፃነትና መደራጀት

የሃሳብ ነፃነትና መደራጀት በሕገ መንግስቱ ሰነድ ቁልጭ ብለው ከተቀመጡት መሰረታዊ” ሰብኣዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ መብቶች ከወረቀት አልፈው በመሬት ላይ አይታዩም፡፡ ሕጉ ለባለሰልጣናት እንጂ ለሰፊው ህዝብ ባዕድ ነው፡፡ ሕጉ የአንድ ድርጅት የበላይነት ጠባቂና መሳሪያ እንጂ የህዝቡንና የሀገሪትዋን ሉአላዊ ክብር የሚጠብቅ ሞሶሶ አይደለም፡፡ ሕጉ ሌሎችን በተለይም በጠላትነት ለሚያዩዋቸው ተቃዋሚ ድርጅቶችን ለመምታት” ለማሳደደድ” ለማሰርና ለማዳከም የሚጠቀሙበት ትልቁ መሳሪያ እንጂ ለእኩልነትና ለፍቅር የቆመ አይደለም፡፡ በሌላ አነጋገር የዳኝነት” የፍትሕ” የምርጫና ሌሎች የዴሞክራሲ ተቋማት የአንድ ድርጅት አገልጋይና መሳሪያ በሆኑበት” ባጠቃላይ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ኢሕአዴግ የተለየ ሃሳብ ያላቸውን ዜጎች እንደባላንጣ ፈርጆ ሰበብ አስባብ እየፈለገ በመምታት ራሱን አውራ ፓርቲ ነኝ ብሎ የሰየመ አምባ ገነናዊ ስርዓት በነገሰበት ሀገር ስለ የሃሳብ ነፃትነትና መደራጀት ብሎ ማንሳት አይቻልም፡፡ በተለይም አሁን ከአቶ መለስ ዜናዊ ህልፈት በሗላ ብሶበታል፡፡ በተለይም የመለስ ራእይ ወራሽ ነን የሚሉ ቡድኖችና ባለስልጣናት ራሳቸው በራሳቸው መተማምን አቅቷቸው ሁሉም ነገር በአንድ ፓርቲ ቁጥጥር ስር መሆን አለበት በሚል ጭፍን አስተሳሰብ ላይ በመመስረት ያለ ምሕረት እየጠረጉ ወደ ፍፁም ጠቅላይ (ቶታሊቶሪያን) የሆነ ስርዓት ተሸጋግሯል፡፡

ከዚህ በመነሳት ዛሬ በሀገራችን ሰላማዊና ሕጋዊ የትግል መንገድ ተከትለው ሕጋዊ ፈቃድ አውጥተው በመንቀሳቀስ ላይ በሚገኙ ተቃዋሚ የፓለቲካ ድርጅቶች ላይ እየደረሰ ያለው አፈናና ወከባ ይህን ነው ብሎ ለመናገር ይከብዳል፡፡ ባንድ በኩል ፈቃድ እየሰጠ በሌላ በኩል ደግም ህገ መንግስት የሰጣቸውን መብት እንዳይጠቀሙ በመከልከልና ብሎም በመገደብ መፈናፈኛ አሳጥቷቸዋል፡፡ ከህዝብ ጋር እንዳይገናኙ” አባላት እንዳይጠጉዋቸው” ህዝባዊ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ እንዳያደርጉ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መሰናክል በመፍጠር የተለያዩ ፀረ ዴሞክራሲና ኢፍትሓዊ የሆኑ እርምጃዎች እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡ ሕብረተሰቡን በተለይም አዲሱ ትውልድ ለለውጥ ሊያነሳሱ ይችላሉ ብሎው የሚገምትዋቸው በአመራር ላይ የተቀመጡ ወጣት ምሁራን ላይ ሆን ብሎው በማነጣጠር በፀረ ሽብር አዋጅ እያመኻኙ ማሰር ስራዬ ብሎው ተያይዞውታል፡፡

ድርጊቱ ደረጃው ይለያይ ይሆናል እንጂ በሁሉም አካባቢ በሁሉም ተቃዋሚ ድርጅቶች ላይ የሚፈፀም ቢሆንም በተለይም ዓረና ትግራይ በሚባል በትግራይ ውስጥ በህግ ተፈቅዶለት በሚንቀሳቀስ ድርጅት ላይ እየተፈፀመ ያለው ግፍ እንደ ምሳሌ ወስደን ብናይ በመላ ሀገሪቱ ያለው አስከፊ የፓለቲካ ደባብ ትክክለኛ ገፅታ ማሳያ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ ድርጅቱ በይፋ በሕግ ከተቋቋመ ጀምሮ አቅሙ በፈቀደው መጠን ይንቀሳቀሳል፡፡ ድርጅቱ የተፈጠረበት ሁኔታ መለስ ብለን ስናይ ትግራይ “የተለየ አመለካከት የያዘ ትግርኛ ተናጋሪ ቀርቶ የተለየ መልክ ያላት ወፍ እንኳን ዘወር አትልበትም በማለት ለአርባ ዓመታት ያህል የህወሓት ትልቁ መደበቂያ ምሽግና ብቸኛ የጓሮ አትክልት ሆኖ በቆየው ምድር ላይ” በመሆኑ ለዓመታት ያህል ስር የሰደዱ የተለያዩ የመጨቆኛ መረቦችንና ሞኖፓላዊ አስተሳሰቦችን ሰብሮ የመርፌ ቀዳዳን የምታህል መንገድ አልፎ በምትኩ ዴሞክራሲያዊና የሰለጠነ ራእይ ይዞ ወደ ሕብረተሰቡ ለመግባት ምን ያህል አስቸጋሪና ውስብስብ ትግል የሚጠይቅ መሆኑን ለመገመቱ አያዳግትም፡፡

ወደ ጠንካራ ሀገራዊ ድርጅት መፈጠር እንደ መሳለል ሆኖ ያገለግላል ተብሎ በሚሊኖች ዘንድ ተስፋ የጣለለት ዓረና በትግራይ አማራጭ ፓርቲ በመፈጠሩ የሚያስደነግጣቸውና እንደ ትልቅ ስጋት የሚያዩት የህወሓት መሪዎች ብቻ አይደሉም፡፡ ሌሎችም የኢትዮ}ያ መፈራረስና ጥፋት የሚመኙ በተለይም በትግራይ በትግራይ ምድር ላይ ኢትዮ}ያዊነት ማንነትና ሀገራዊ ራዕይ የሰነቁ ለህዝቦችዋ አንድነትና ክብር የሚሟጎቱ ሀገር በቀል ብሄረተኞች እንዳይበቅሉ የሚሰጉ እንደ ሻዕቢያና ጀሌዎቻቸው የመሳሰሉት ሀይሎች ይህቺን ባቄላ ካደረች አትቆረጠምም በማለት ዓረና ትግራይን ከእንጭጩ ለማጥፋትና ለማዳከም የዘወትር ተግባራቸውና ሕልማችው መሆኑን ህዝቡ ከጥዋቱ ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ሌላውን ትተን በቅርቡ የብዙሃን መገናኛዎችንና ማህበራዊ ድህረ ገፆችን እየተጠቀሙ በዓረና አባላትና መሪዎቹ ላይ የተቀናጀ ጥቃት ለመፈፀም ምን እያሉ እንደሆነ በቀላሉ መገንዘብ ይቻላል፡፡ የሚገርመው አንዳንዶቹ እንዲያውም ለነገሩ ለይስሙላ ተቃዋሚዎች ነን ይበሉ እንጂ በተግባር ሲታይ ስውር አጀንዳቸው ከህወሓት/ኢሕአዴግ በላይ ዓረና ትግራይን እንደስጋት የሚያዩት መሆናቸውን በግልፅ የሚያመላክት ነው፡፡ ሆኖም ሀቁ “እኛም አውቀናል ጉድጓድ ጭረናል” እንደተባለው ሁሉ ጭቆና ያንገሸገሸው ህዝብ ነፃ እስካልወጣ ድረስ ይቅርና የወሬ ጋጋታ ሚሊዮን ጦርም ቢሰለፍ ከመታገል ወደሗላ ሊመልሰው የሚችል ምድራዊ ሀይል እንደማይኖር ሊያውቁት በተገባ ነበር፡፡

ከዚህ የተሳሳተ አመለካከትና ግምት በመነሳት በተለይም በመንግስት በኩል የዓረና ትግራይ ፓርቲ አባላት ለሆኑ ዜጎች የሚደርስባቸው ጫና” ግፍና አፈና ለመቀበል አይደለም ለማሰብም በጣም ያስቸግራል፡፡ ካድሬዎቹ ራሳቸው ከሳሽ” ራሳቸው መስካሪ” ራሳቸው ዳኛና አሳሪ እየሆኑ ማሰቃየት” ከህብረተሰቡ እንዲገለሉ ማድረግ” ከስራ ማባረር” ሀገር ያፈራውን ጥቅማ ጥቅም መከልከል የተለመደ ስራ ሆኗል፡፡  የትምክህት ሀይሎች አመለካከት አራማጆች” እንዲሁም በነሱ አጠራር አሸባሪዎችና ታሪካዊ ጠላቶቻችን ናቸው ከሚሉዋቸው ጋር በማዛመድ ተላላኪዎችና ወኪሎች ናችሁ” በመባል እየተወነጀሉ አብረው የጥቃቱን ሰለባ እንዲሆኑ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህ የተነሳም ማሕበራዊ ቀውስና ጫና እየደረሰባቸው ያበዱ ወይም የት እንደገቡ የማይታወቁ የድርጅቱን አባላት ቁጥራቸው ቀላል አይደለም፡፡ በዚህ ዓይነት በተመሳሳይ እየተከሰሱና እየተጠረጠሩ ቤታቸው የፈረሰ ቤተሰብ” የተፋታ ትዳርና ሳይወድ በግድ ከሞቀ ቤቱና ከቀዩ እየፈለሰ ወደ ስደት የሚጎርፈው ወጣት ቤቱ ይቁጠረው፡፡ ለአብነት የሚከተሉትን ግለሰቦች የደረሰባቸው ግፍ እንመልከት፡፡

  • መምህር ሀይሌ አሰመኽኝ የሚባል የህወሓት የቀድሞ ታጋይ የነበረና በሗላም በባድመ ጦርነት የቀኝ እጁን ተቆርጦ ወደ ቤቱ የተመለሰው ወገን የአረና ትግራይ አባል በመሆኑ ብቻ በአካባቢው ካድሬዎች በተደረገበት ክትትልና ወከባ ምክንያት እንዲያብድ ተደርጎ አሁን የት እንዳለ አይታወቅም፡፡ ቤተሰቡም ድርብ ድርብርብ ሃዘን ሆኖባቸው እያለቀሱ ይገኛሉ፡፡ በሸራሮ ከተማም በተመሳሳይ አካሃን አቶ ፍፁም ያሃንስ በሚባል ወገናችን በደረሰበት ተፅእኖ አብዶ የከተማው ህዝብ መቀጣጫ ሆኖ ይገኛል፡፡

 

  • በዛና ከተማ እና አካባቢዋ በጣም ታዋቂ የነበረው የድሮ የህወሓት ታጋይ ዛሬ የአረና አባል በመሆኑ ብቻ ካድሬዎቹ ሲከታተሉት ከቆዩ በሗላ እሱን የሚያጠቁበት የተለያየ ምክንያት በመፈለግ በቤተሰቡ ላይ ጫና በመፍጠርና በመካከላቸው ጣልቃ በመግባት የገዛ ዘመዶቹና ቤተሰቦቹ ሳይቀሩ እንዲከሱት እና ተባባሪ እንዲሆኑ በማድረግ በደረሰበት ተፅእኖ ከቤቱና ከቀዩ እንዲባረር ተደርጎ አሁን አዲስ አበባ ይገኛል፡፡ ይህንን እውነታ በግልፅ የነገረኝ ስሙን እንዲጠቀስ ያልፈለገው የመንግስት ሰራተኛ የሆነው የራሱ ወንድም ነው፡፡

 

  • ሌላ አንድ ወጣትም ተመሳሳይ ፈተና ገጥሞታል፡፡ ልጁ የአረና አባል አይደለም፡፡ ነገር ግን አንድ ቀን ወጣቱ ከአንድ የአረና ትግራይ አባል በመንገድ ተገናኝተው ቆሞው ሲያወሩ እንደአጋጣሚ ሆኖ ሌላ አንድ የሚያውቀው ልጅ ሰላም ብሎት አብሮት ትንሽ መንገድ ይጋዛል፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በሗላ ልጁ ወደ ስራ ቦታው ሄደና ገና ስራ ከመጀመሩ በፊት ለካስ መረጃ ተላልፎ ቆይቷል በአስቸካይ አስተዳደር ጋር ይጠራል እና ይገባል፡፡ ሃላፊውም “ከመቼ ጀምረህ ነው የአረና ትግራይ አባል የሆንከው?” ብሎ ድንገተኛ ጥያቄ ይጠይቀዋል፡፡ “የማናውቅ እንዳይመስልህ እውነቱን አውጣ” ብሎ ያስፈራራዋል፡፡ ልጁም በድንጋጤ የአረና አባል እንዳልሆነ ቢገልፅለትም ሃላፊው በፍፁም ሊቀበለው አልቻለም፡፡ እናም ከዛ በሗላ ከባድ ማስጠንቀቅያ ተሰጥቶት ወደ ስራው ተመልሷል፡፡

የልጁ አባትም አብረውት በዚሁ መስሪያ ቤት ውስጥ በዘበኝነት ተቀጥረው ይሰራሉ፡፡ አባትየውም በተመሳሳይ ተጠርተው ልጃቸው ዓረና እንደሆነ እና ስራቸው አደጋ ላይ ሊወድቅ እንደሚችል ተነግረዋቸው እሳቸውም ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶዋቸው ወደ ስራቸው ይመለሳሉ፡፡ ሁለቱም ማታ በቤት ከተገናኙ በሗላ አባትየው ልጃቸውን ቁጭ አድርገው የዓረና አባል መሆኑን እና አለመሆኑን ሲጠይቁትና ሲመረምሩት አመሹ፡፡ እሱም እንዳልሆነ ገለፀላቸው፡፡ በመጨረሻ አባትየው “በል ስማ ከዚህ በሗላ የአረና ትግራይ አባል ሁነህ ካገኘሁህ ግን ሰው ያላደረገውን ባንተ ላይ አደርጋለሁ” አሉት፡፡  ልጁም ገርሞት “ምን ታደርጋለህ አባዬ” ብሎ ሲጠይቃቸው እገድልሃለሁ አሉት በገዛ ልጃቸው፡፡ ይህን ቃል የነገረኝ ራሱ ልጁ ከጋደኞቹ ፊት ቁጭ ብለን ስናወራ ነው፡፡  ልጁ አሁን በአዲስ አበባ ከተማ በደህና ቦታ ተቀጥሮ እየሰራ የሚገኝ የመንግስት ሰራተኛ ነው፡፡ አሁን ልጁ ለስርዓቱ ያለውን ታማኝነት ለመግለፅና እንዲሁም ከአባቱ ጋር ተግባብቶ ለመኖር ሲል በማያምንበት ጉዳይ በየቀኑ ህወሓትን ደግፎ በየፌስቡኩ ሲሳደብ ይውላል፡፡

አብርሃ ደስታ

ለረጅም ጊዜ በቅርብ ርቀት ሲከታተሉት ከቆዩ በሗላ የመንግስት ጣት ተቀስሮባቸው የስርዓቱን የአፈና ሰለባ ከሆኑት ሰላማዊ ታጋዮች አንዱ በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የፓለቲካ ሳይንስ መምህር የሆነው ወጣት አብራሃ ደስታ ነው፡፡ ከመታሰሩ ጥቂት ቀናት በፊት በስልክና በአካል በመቐለ ከተማ ተገናኝተን አብረን ቁጭ ብለን በሰፊው እንድናወራ እና ይበልጥ ማንነቱን እንዳውቀው እድል አግኝቼ ነበር፡፡ አብራሃ በፅሁፍ እና በአካል ስታየው በጣም ይለያያል፡፡ ከምጠን በላይ ትሁት” ሕግና ስነ ስርዓት አክባሪ ሰው ነው፡፡ ረጋ ብሎ የመናገር እና የማስረዳት ችሎታው ከፍተኛ ነው፡፡ ተግባቢ ነው፡፡ አድማጭ ነው፡፡ በፍፁም አይጠጣም አያጤስም፡፡ ለስላሳ ይደግማል፡፡ በዩኒቨርሲቲው ማሕበረሰብ ዘንድም በስራ ችሎታቸውና በሞያ ብቃታቸው ከሚደነቁትና ከሚከበሩት ሰዎች አንዱ ነው፡፡

አብርሃ ደስታ ለሰላማዊና ሕጋዊ ዴሞክራሲያዊ ትግል ያለው ፅናትና እምነት በቃላት ብቻ ሳይሆን በተግባርም በሄደበት ሁሉ በህዝባዊ ስብሰባም ሆነ በግል ሲወያይ በሰላም ታግሎ እንዴት ለውጥ ሊመጣ እንደሚችል ሲያስተምር ቆይቷል፡፡ በስብሰባ በህዝብ ፊት ቀርቦ የማሳመን ችሎታውም ከሞያው ብቃት ተዳምሮ ዘመን የፈጠረው ታጋይ እየተባለ በብዙዎቹ ዘንደ ይነገርለታል፡፡ ብቃቱንና ፅናቱን የቀድሞ የአረና ትግራይ አመራር የነበረው እና በሀገራዊ ምርጫ ዋዜማ ባልታወቀና በረቀቀ ሁኔታ በጭካኔ የተገደለው የወጣቱ ታጋይ አረጋዊ ገብረዮሐንስ ወኔ ወራሽ ነው እየተባለ ይነገርለታል፡፡

አብርሃ ደስታ ህወሓትን በሃሳብ እንደተሸነፈና ከመሳደብ” ከማሸበርና በጉልበት ከማሰር በስተቀር በህዝብ ፊት በአደባባይ ቆሞ በሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ በግልፅ ለመወያየት የሞራል መሰረትና ብቃት የሌለው የበሰበሰ ድርጅት መሆኑን በግልፅ ይናገር ነበር፡፡ይህም ህወሓቶች የተለየ ሃሳብ ይዞ በግልፅ መወያየት ያልለመዱት የፓለቲካ ባህል ስለሆነ እንደድፍረት በመቁጠር ጥርስ ተነክሶበት ከቆየ በሗላ እንደተለመደው አብርሃ ደስታን የሚያጠምዱበት ቀንና አጋጣሚ ሲከታተሉና ሲጠብቁ ከርሟል፡፡

በመጨረሻም ከትግል አጋሮቹ ጋር ቁጭ ብለን እያወራን እያለ ስለ የስርአቱን ምንነት” ያለው ክፋትና አፈና ከባህሪያቸው ጋር አያይዞ ብዙ ዝርዝር ነገሮች አወሳልን፡፡ ስለራሱ የግል ጉዳይም በማንሳት ከአንድ የደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ ጋር የዶክትሬት ፕሮገራም ይከታተል እንደነበረ እና በማያውቀው ሁኔታ ስለተቋረጠ ወደ ሚመለከተው አካል ሄዶ መማር እንዳልቻለ ነገረን፡፡  ለምን እንደተቋረጠ ቢጠይቅም ባለስልጣኑ በፌዝ “አንተ ስለ ትምህርት ታወራለህ፡፡ ያንተ መማር ይቅርና ሌሎቹ ካንተ ጋር ሰላምታ የሚለዋወጡ ሰዎችም ጭምር አደጋ ላይ ናቸው፡፡” ብሎ እንደ መለሰለት ነገረን፡፡ ከዚያቺ ደቂቃ ጀምሮ አብርሃ እንደሚያስሩት አስቀድሞ ያውቅ ነበርና ቁጭ ብለን በጋራ ስናወራ የአብርሃ ደስታን ፓለቲካዊ ብስለት ከሚናገራቸው ቃላት በላይ ከፊቱ የሚነበበው ልበ ሙሉነት” የአላማ ፅናትና ድፍረት ይታይበት ነበር፡፡ እንደሚያስሩት እያወቀ ምንም የፍርሃት መንፈስ ወይም ስጋት አይታይበትም፡፡ እኔም ገረመኝ፡፡ ለማመንም ከብዶኝ ነበር፡፡

አዎ!! በኔ እምነት በማስረጃ ላይ የተደገፈ ነገር ካለ አንድ ሰው ሕግ ፊት መቅረብ የለበትም የሚል ጭፍን እምነት የለኝም፡፡ ነገር ግን ዜጎች የተለየ እምነት ስለያዙ ብቻ ለአንድ ድርጅት የፓለቲካ ጠቀሜታ ተብሎ (politicaly motivated) ወይም በቂም በቀል (Revenge) ተነሳስቶ በሰላማዊያን ዜጎች ላይ የሚፈፀም የስም ማጥፋትና የክስ ሂደት ድራማ ግን ሕገ ወጥ ድርጊት ብቻ ሳይሆን በኢትዮያዊነታችን የርህራሄ ባህላችንም አኳያ ሲታይ ኢሰብኣዊነት” ከሃላፊነትና ከስነ ምግባር ውጭ ስለሆነ አልደግፈውም ብቻ ሳይሆን መወገዝ ያለበት ነው፡፡

በዚሁ መለኪያ በአብርሃ ደስታ ላይ የተፈፀመ እንግልትና እስር ሲታይ ከነ ብርቱኳን ሜደክሳ እና ሌሎች በቃሊቲና በማእከላዊ እስር ቤቶች ታጉረው ከሚገኙ የህሊና እስረኞች የሆኑት ወጣት ፓለቲከኞች ወንድሞቻችን ጋር ተመሳሳይነት አለው፡፡ የክሱ ቀደም ተከተልና አካሄድ ስናየው ሕጋዊ መሰረትና እውነትነት የሌለው መሆኑን የሚያሳየው መጀመሪያ እንደ እንስሳ በጉልበት መደብደብ” ከዚያ በሗላ ማሰር” ከተደበደቡና ከታሰሩ በሗላም ከዳኝነት በፊት ከሰብኣዊ አያያዝ ውጭ ለፐሮፓጋንዳ ጠቀሜታ ሲባል በቪድዮ እየቀረፁ ለፓብሊክ ማጋላጥ፡፡  ከዚያም ቀጥሎ ለይስሙላ ማስረጃ ፍለጋ መሄድ ሲሆን የመጨረሻ ዕድላቸው ደግሞ በወህኒ ቤት እንዲበሰብሱ ወይም የይቅርታ ወረቀት እንዲፈርሙ በማድረግ የትግል ወኔያቸው አኰላሽቶ መልቀቅ ነው ፡፡ ይህ የዜጎች ሰብኣዊ ክብርና ሕገ መንግስታዊ መብት የሚዳፈርና የሚፃረር” ከአንድ መንግስት ነኝ ከሚል አካል የማይጠበቅ ሕገ ወጥ ተግባር ከመሆኑም በላይ ኢትዮ}ያ የፈረመችባቸው ዓለም አቀፍ የሰብኣዊ ፍጡርና የሕግ እስረኞች አያያዝ ሕግጋትም የሚጥስ ነው፡፡

 

አብርሃ ለምሳሌ ያህል ጠቀስኩት እንጂ በሌሎች ክፍላተ ሀገር በወጣት ታጋይ ወንድሞቻችን ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃም አላማው ተመሳሳይ ነው፡፡ በኢትዮ}ያ በሀገር ደረጃ የትግል አንድነት እየተፈጠረ ከሄደና ወጣት ምሁራን ወደ ትግሉ እየተቀላቀሉና የፓለቲካ አመራሩን እየተኩ ከሄዱ ለህወሓት/ኢሕአዴግ ትልቅ ስጋትና የፓለቲካ ኪሳራ ነው ከሚል ስሌት የመነጨ የፍርሃት እርምጃ መሆኑን ያዳባባይ ሚስጢር ነው፡፡

የሚገርመው ግን ህወሓቶችና ኢሕአዴጎች በወገን ላይ አፈናና ግፍ መፈፀማቸው ብቻ አይደለም፡፡  ነገር ግን አምባ ገነኖች የህዝብ እሮሮና ብሶት የዶሮን ያህል ግምት ሳይሰጡ በሰራዊት ጉልበት” በጦር መሳሪያ ጋጋታና ክምር ተማምነው ግለሰቦችንና ታጋዮችን ባሰሩና ጭቆናውን እያከረሩ በሄዱ ቁጥር የህዝቡን ልብ የበለጠ እንዲሸፍትና ሽዎች ታጋዮች እንዲፈልቁ ያደርጋል እንጂ ትግሉን ማዳፈን እንደማይቻል ካለፈው ታሪክ ሳይማሩ አሁንም ተመሳሳይ ድራማ መስራታቸውን ነው፡፡ እንዲህ ከቀጠለ ደግሞ ወደዱም ጠሉም ዕድሜያቸውንም በዚያው መጠን እያጠረ መሄዱ የማይቀር ተፈጥራዊ ሂደት መሆኑንም በውል ሳይገነዘቡ መቅረታቸው ነው የሚያሳዝነው፡፡

ከላይ የተጠቀሱትን የመልካም አስተዳደር እጦት መንሲኤያቸው ሁሉም ከአንድ ወንዝ የሚቀዱ ናቸው፡፡ ይህ ማለት በሀገሪቱ ውስጥ ካለው ጠባብ የፓለቲካ ምሕዳር የሚመነጩ ናቸው ማለት ነው፡፡ የህወሓት/ኢሕአዴግ ስርዓት የህዝቡን መሰረታዊ ችግሮች ሊፈታ የማይችል” ዴሞክራሲያዊ ባህርይ የሌለው” መሰረቱን የተናደና የተፋለሰ ፓሊሲ የሚከተል በመሆኑ ብቻ የሚመነጩ ችግሮች ናቸው፡፡ መፍትሔውም የግለ ሰዎች መቀያየር ሳይሆን መሰረታዊ የአስተሳሰብ” የፓሊሲና የስርዓት ለውጥ ያስፈልገዋል ብዬ በፅኑ አምናለሁ፡፡ በኔ እምነት ማን ስልጣን ላይ ወጣ አይደለም ችግሬ፡፡  ዋናው ቁም ነገሩ ማን ምን ዓይነት ለህዝብ የሚጠቅም የፓለሲ ለውጥ ይዞ መጣ ነው መመዘኛዬ፡፡

ውድ ወንድሞቼና እህቶቼ

ከላይ በመጠኑም ቢሆን የጠቀሱኳቸው ነጥቦች ብዙዎቻችሁ እንደምትጋሩ እምነቴ ነው፡፡ በተለይም እኔም ባልሳተፍኩበት በዚሁ ዓመት አጋማሽ ላይ የትግራይ ክልላዊ መንግስት ያዘጋጀውን ፌስቲቫል ለመካፈል ከዲያስፓራ ወደ ትግራይ ክልል ሂዳችሁ በነበረበት ጊዜ ባለስልጣናቱ የህዝብ አዛኝ መስለው ለመታየት ሲሉ ቃጤማ አንጥፈው ለመቀበል ሙከራ ቢያደርጉም የህዝቡን እሮሮና መከራ ግን ለመሸፈን ስላልቻሉ በሕብረተሰቡ ውስጥ ማለት በመሬት ላይ ያለውን እውነታ ተገንዝባችሁ በየስብሰባውና በተናጠል ሲቀርቡ የነበሩ ጥያቄዎች የብዙዎቻችን ጥያቄ መሆናቸውን እገነዘባለሁ፡፡ በተጨማሪም ሰሞኑን በዓይጋ ድህረ ገፅ ላይ አባይ ወልዱ ሙሱናን በሚመለከት ሁለት ሽሕ ለሚሆኑ ካድሬዎች ሰብስቦ ያቀረበውን ካንገት በላይ ንግግር አስመልክቶ ህዝቡ የሚሰማውን ሃሳቡ እንዲሰጥ ተብሎ በተከፈተው የአስተያየት አምድ ላይ ከተሰጡት በመቶ የሚቆጠሩ አስተያየቶች ውስጥ አብዛኞቹ ቀደም ብዬ በክፍል አንድ ያቀረብኩትን ፅሑፍ በበለጠ የሚያጠናኩሩልኝ ሆነው በማየቴ ትእዝብታችን ብቻ ሳይሆን ብሶታችንም አንድ ዓይነት መሆኑን ለመገንዘብ ችያለሁ፡፡ የተሰጡ አስተያየቶችም በህዝባችን ላይ የተጫነው ሸክምና የተጋረጠው ቁስል በብዙዎቻችን ሆድና አእምሮ ውስጥ የታመቀ ብሶት ገንፍሎ እንደወጣ የሚያሳይ ሲሆን በሌላ መልኩ ደግሞ የጊዜ ጉዳይ እንጂ በልቡ የሸፈተ ህዝብ እንዳለ ቁልጭ አድርጎ የሚያመላክት ነው፡፡

አዎ!! የቀረቡት ወርቃማ አስተያየቶች” ጥያቄዎችና የለውጥ ፍላጎቶች ሁሉ ትልቅ ትርጉም ያላቸው ቢሆኑም ውጤት የሚኖረው በአግባቡ ተገንዝቦና አጢኖ መልስ ለመስጠት የሚችል የሚሰማ ጆሮ” ከጊዜው ጋር የሚመጥን አእምሮ” የህዝብንና የሀገርን ጉዳይ የሚያስቀድም ዴሞክራሲያዊ ተፈጥሮ ሲኖር ብቻ መሆኑን የግድ ይላል፡፡ ይህ ባለቤት ያጣ ሚስኪን ህዝባችን ከአፈና” ከፍርሃት” ከፍልሰትና ከውርደት ተላቆ የነፃነት አየር የሚተነፍስበት ስርዓት እንዲፈጠር ሁላችንም የሃሳብ ልዩነታቸንና ሕብረ ቀለማችንን እንደ ውበትና ፀጋ ተቀብለን በሚያገናኙን ጉዳዮች ዙሪያ ለጋራ ችግር በጋራ ለመፍታት ተባብረን መቆምና መጮኽ እንዳለብን ጊዜውም ራሱ እየተናገረ ነው፡፡

ቸር ይግጠመን

የዛሬው ፅሑፌ በዚሁ ይጠቃለላል፡፡ በሚቀጥለው የመጨረሻው ክፍል 3 ፅሑፌ የአቶ መለስ ዜናዊ አምልኮ በሕብረተሰቡ ዘንድ እየፈጠረ ያለው የስነ ልቦና ጫናና ሌሎች አንገብጋቢ ጉዳዮችን በማካተት ይቀርባል፡፡

 

sgbtsait@gmail.com

 


Sport: የትንንሾቹ የአትላንቲክ ደሴቶች የእግር ኳስ ወግ –የሴንት ሄሌና ደሴት ነዋሪዎች 4000 ብቻ ናቸው

$
0
0

- የሴንት ሄሌና ደሴት ነዋሪዎች 4000 ብቻ ናቸው
– በደሴቶች ኦሎምፒክ ለመሳተፍ ይፈልጋሉ

የምናወቀው እግርኳስ በእጅጉ እየተለወጠ ነው፡፡ በዓለም እግርኳስ የቲኬት ዋጋ በእጅጉ እየናረ ነው፡፡ ቢሊየነር የክለብ ባለቤቶች ተጨዋቾችን ለማዘዋወር እና ለደመወዝ አስደንጋጭ የሆነ ከፍተኛ ገንዘብ እያወጡ ነው፡፡ ሆኖም በደቡብ አትላንቲክ ውቅያኖስ በሚገኙ ደሴቶች እግርኳስ የሚጠበቅበትን ስራ እየተወጣ ነው፡፡ ማህበረሰቦችን ወደ አንድነት ማምጣት፡፡
Soccer logo 2014 2
ሴንት ሄሌና በጣም የምትታወቀው ለፈረንሳይ የቀድሞ መሪ ናፖሊዮን ባናባርቴ የስደተኝነት መዳረሻ በመሆን ነው፡፡ ፈረንሳዊው 1821 ህይወቱ ያለው በዚህች ደሴት ነው፡፡ ደሴቷ ጠባብ ነች፡፡ የሴንት ሄሌና ህዝብ ቁጥር ከ4000 አይበልጥም፡፡ ይህ ቁጥር ይበልጥ መቀነሱ ደግሞ አይቀርም፡፡ ምክንያቱም ወጣቶቹ የደሴቷ ነዋሪዎች ለትምህርት እና ለስራ ወደ ብሪታኒያ እያመሩ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ብዙም አያስደንቅም፡፡ ምክንያቱም የሀገሪቱ ሠራተኞች ዓመታዊ አማካይ ደመወዝ 5500 ፓውንድ ብቻ ነው፡፡ ሆኖም በርካታ ችግሮች ቢኖሩበትም ሴንት ሄሌና የእግርኳስ ሊግ አላት፡፡ የእግርኳስ ማህበርም እንዲሁ፡፡
የሴንት ሄሌን የእግርኳስ ሊግ በሜይ ወር ይጀመራል፡፡ የክሪኬት የውድድር ዘመን የሚጀመረው የሊግ ማብቂያ ላይ ነው፡፡ ሴንት ሄሌና የምትመራው በብሪታኒያ ነው፡፡ ሊጉ እጅግ ከባድ ፉክክር ይደረግበታል፡፡ ተመልካቾችም ሊጉን በትኩረት ይከታተላሉ፡፡ የ2014 ሊግ 12 ክለቦች ይሳተፉበታል፡፡ እስካሁን ድረስም ከፍተኛ ፉክክር እየተደረገበት ነው፡፡ ሪቨርስ እና ሀርትስ የተባሉ ክለቦች ለሻምፒዮንነቱ እየተፎካከሩ ነው፡፡ ያለፈውን የውድድር ዘመን ሻምፒዮኖቹ የሴንት ሄሌና ዋየርበርድስ ጥሩ ጊዜን እያሳለፉ ባይሆንም በሊጉ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ ኮከብ ተጨዋቻቸው ጀንሰን ጆርጅ ደግሞ የከፍተኛ ጎል አግቢነቱን ደረጃ እየመራ ነው፡፡ እስካሁን 17 ጎሎችን አስቆጥሯል፡፡

ሴንት ሄሌና በኢንተርናሽናል እግርኳስ የመሳተፍ ህልም አላት፡፡ የደሴቷ እግርኳስ ማህበር ለ2011ዱ የደሴቶች ውድድር አንድ ቡድን ለመላክ አስባ ነበር፡፡ ውድድሩ የኦሎምፒክ መርህን የተከተለ ሲሆን በመላው ዓለም የሚገኙ ደሴቶች የሚሳተፉበት ነው፡፡ የ2011ዱ የደሴቶች ጨዋታዎች የተከናወነው በአይሰል ኦፋዌይት ነበር፡፡ እግርኳስ ማህበሩ 17 አባላት የያዘ ስኳድ ለመላክ እቅድ ነበረው፡፡ አምስቱ ከደሴቷ የሚመረጡ ሲሆን ሌሎች ደግሞ በዩናይትድ ኪንግደም የሚገኙ የሴንት ሄሌና ዝርያ ያላቸውን ተጨዋቾች ለማድረግ ታስቦ ነበር፡፡ ሆኖም ይህን እቅድ ማሳካት አልተቻለም፡፡ ህልሙ እውን መሆን ያልቻለው በፋይናንስ ችግሮች ምክንያት ነበር፡፡

የሴንት ሄሌና እግርኳስ ማህበር በቅር ከዓለም አቀፉ የእግርኳስ አስተዳዳሪ ፊፋ ጋር ግንኙነት ፈጥሯል፡፡ ሌላኛው በብሪታኒያ የተያዘው ጄብሪልተር የአውሮፓ እግርኳስ ማህበር የፊፋ አባል የማይሆንበት ምክንያት እንደሌለ ያሳያል፡፡
ሆኖም የትሪስተን ዳ ኩንሃ ደሴት ጉዳይ ከበድ ይላል፡፡ በእሳት ጎመራ በፍንዳታዎች የምትታወቀው ደሴት ከሴንት ሄሌና 1600 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ በትሪስተን ዳ ኩንሃ የሚገኙት ነዋሪዎች ቁጥር 300 ብቻ ነው፡፡ በአሳሹ ትሪስተኑ ዳ ኩንሃ ስም ለተሰየመችው ደሴት ነዋሪዎች እግርኳስ ዋነኛ የህይወታቸው አካል ነው፡፡ ስለ እግርኳስ አውርተው ከማይጠግቡት የደሴቷ ነዋሪዎች አንዱ ሊዮን ግላስ ነው፡፡ የደሴቷን የመጀመሪያ እና ብቸኛ የእግርኳስ ክለብ የመሰረተው ሊዮን ነው፡፡ ትሪስተን ዳ ኩንሃ ኤፍሲ ይሰኛል፡፡

‹‹የቴሌቪዥን ስርጭት በስፖርት ያለውን ፍላጎት በጨመረበት ወቅት የትሪስትን እግርኳስ ቡድን በ2002 ተቋቋመ›› ይላል ግላስ፡፡ ‹‹ለጉብኝት የሚመጡ ተጋጣሚዎችን ስናገኝ ከተቃራኒው ቡድን ጋር እንጫወታለን፡፡ በቅርብ ዓመታት ግን የመጡ ቡድኖች የሉም፡፡ ተጋጣሚዎች ስለሌለ ተጨማሪ ቡድኖችን ማቋቋም የሚችል አይመስለኝም፡፡ በዚያ ላይ ያለውን ቡድን ለመቀላቀል የሚፈልጉ ሰዎች ቁጥም ቀንሷል፡፡ ትረስትን ዳ ኩንሃ ኤፍሲ በዓለም እጅግ ሩቅ ቦታ የሚገኘው ክለብ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ምንም እንኳን ከዚህ በፊት ግጥሚያዎችን አድርገው ቢያውቁም (ከመርከብ ሰራተኞች ጋር ተጫውተው ያውቃሉ) ክለብ የሚገኝበት ቦታ ርቀት ጎድቷቸዋል፡፡ እንደ ሴንት ሄሌና ሁሉ ሊዮን ግለስም አንድ ቡድንን ወደ ደሴቶች ኦሎምፒክ ለመላክ ፈልጎ ነበር፡፡

‹‹እንደ ቡድን ወደ ደሴቶች ኦሎምፒክ ለመላክ ተወያይተንበት ነበረ፡፡ ነገር ግን ለጉዞው የሚያስፈልገውን ወጪ ለመሸፈን አቅም አልነበረንም፡፡ ገንዘብ እና ዕድል ካገኘን ከፍለን ወደ ውጭ ሀገራት መውሰድ እንፈልጋለን›› እያለ ሊዮን ያሉትን ችግሮች ያስረዳል፡፡ ዕድል ግን አልቀናቸውም፡፡ ተጋጣሚ ማጣታቸው ቡድኑን ወደ መፍረስ ደረጃ ሊያደርሰው ተቃርቧል፡፡ አሁን ባለ አምስት ተጫዋቾች ቡድን ሆኗል፡፡ ‹‹የዓለም ጫፍ ላይ የሚገኘው ቡድን›› የሚል ትልቅ ስም ያለው ቡድን ቢሆንም እየተቸገረ ነው፡፡ ተጋጣሚ አልባ ቡድን፡፡
ሆኖም በሌላ 1600 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ደሴት ሁኔታው የተለየ አይደለም፡፡ አሴንስን ደሴት 800 ነዋሪዎች ብቻ አሏት፡፡ አብዛኞቹ ነዋሪዎች ደግሞ የአሜሪካ፣ ብሪታኒያ እና ሴንት ሄሌና ዝርያ አለባቸው፡፡ ደሴቷ እንደ ትሪስተን ዳ ኪንሃ እና ሴንት ሄሌና የምትተዳደረው በብሪታኒያ ነው፡፡ በደሴቷ እግር ኳስ እጅግ ተወዳጁ ስፖርት ነው፡፡ አሴንስን የራሷ የእግርኳስ ሊግም አላት፡፡ ሆኖም በደሴቷ እግርኳስ ያለ ችግር አልቆመም፡፡ በደሴቷ ያለው ብቸኛው የእግርኳስ ሜዳ የተሰራው ከባህር ዳርቻ ጎን ነው፡፡ በጨዋታ ቀናት ኤሊዎችን ሜዳ ላይ መመልከትም የተለመደ ነው፡፡ ሜዳው ሣር የሚባል ነገር የለውም፡፡ ነገር ግን እንደ ሴቷ ጋዜጠኛ ካትሪን ሊዮን ከሆነ አዲስ ስታዲየም የመስራት እቅድ አለ፡፡

‹‹አዲስ ስታዲየም መገንባቱ አይቀርም፡፡ አሮጌው ደግሞ ለተወሰኑ ዓመታት ለመጫወት ያስችላል፡፡ ሎንግቢች የእግርኳስ ሜዳ ረጅም ታሪክ ስላለው ሰዎች ለመልቀቅ አልፈለጉም፡፡ አዲስ ስታዲየም ሲገነባ የተሻለ አገልግሎት መስጠት ይችላል፡፡ ሌሎች ስፖርቶችንም ያስተናግዳል፡፡ በትምህርት ቤቱ አቅራቢያ ስለሚሰራም ተማሪዎች በቀላሉ ሊጠቀሙበት ይችላሉ፡፡ ገና በደሴቷ አብዛኛዎቹ ቋሚ ነዋሪዎች አይደሉም፡፡ የሚኖሩትም የሥራ ፈቃድ አውጥተው ነው፡፡ በመሆኑም በደሴቶች ኦሎምፒክ የሚሳተፍ ቡድን ማዘጋጀት ይከብዳል፡፡ ሊጉ ግን ተጠናክሮ ቀጥሏል››
የአሴንስን እግር ኳስ ሊግ ስድስት ቡድኖች ይሳተፉበታል፡፡ ኢንሲትዊነርስ፣ ቱ ቦትስ ዩናይትድ እና ያለፈው የውድድር ዘመን ሻምፒዮኖቹ ቪሲ ሚላን ከተፎካካሪዎቹ መካከል ናቸው፡፡ እግርኳስ እጅግ ተወዳጁ ስለሆነ የደሴቱ ጋዜጣ The inslander የጨዋታ ዘገባዎችንም ትንታኔዎች ይዞ ይወጣል፡፡ ሴንት ሄሌና ሴንቲነል የተሰኘው ጋዜጣ ደግሞ የአሴንሴን ሊግ የአንድ ገፅ ሽፋን ይሰጣል፡፡ የደሴቷ ነዋሪዎች በቁጥር ትንሹ ቢሆንም በየሳምንቱ ቅዳሜ ወደ ሎንግቢች ሜዳ ለጨዋታ ይሄዳሉ፡፡ ሜዳው በኤሊዎች ተሞልቶ ወይም የባህር ውሃ ርሶ ቢያገኙትም ከመጫወት እና ከመመልከት ወደኋላ አይልም፡፡
አሴንስን ደሴትን ለቅቀው ወደ ደቡብ አቅጣጫ ሲጓዙ የፎክላንድ ደሴቶች ያገኛሉ፡፡ ደሴቶቹ በእንግሊዝ እና አርጀንቲና መካከል አስከፊ ጦርነት የተካሄደባቸው ናቸው፡፡ የፎክላንድ ደሴቶች በደቡብ አትላንቲክ ውቅያኖስ ከሚገኙት ሌሎች ደሴቶች የሚለያቸው የራሳቸው ሊግ የላቸውም፡፡ ባለፉት 10 ዓመታት የደሴቶቹ እግርኳስን የሚያስተዳድረው የፎክላንድ ደሴቶች እግር ኳስ እየተዳከ ነው፡፡ በደሴቶቹ እግርኳስን የሚያስተዳድረው የፎክላንድ ደሴቶች እግርኳስ ሊግ በ2011 ሊጉን አፍርቶበታል፡፡ ለመወዳደር የቀሩት አራት ቡድኖች ብቻ ስለነበሩ ነው፡፡ በፎክላንድ ከሪኬት የበለጠ ተወዳጁ ስለሆነ የእግር ኳስ ፍላጎት መዳከም አንደኛው ምክንያት ነው፡፡ ሆኖም ሊግ ባይኖራቸውም ፎክላንድ በደሴቶች ኦሎምፒክ መሳተፋቸውን ቀጥለዋል፡፡ የፊፋ አባል የሆነውን ቤርሙዳ እና ከአውሮፓ እግርኳስ ማህበር አባል ጂብራለታር፣ እንዲሁም አይሰል ኦፍ ማን፣ ጉኤርንሴይ እና ግሪንላንድ ጋርም ተጫውተዋል፡፡ በውድድሩ ያላቸው ሪከርድ አስደሳች አስደሳች ባይሆንም በ2013 በብሪታኒያ በምትተዳደረው ቤርሙዳ በተዘጋጀው የደሴቶች ኦሎምፒክ ላይ ሶስተኛ በመውጣት የነሃስ ሜዳሊያ ተፋልመዋል፡፡ ነገር ግን በፊፋ ደረጃ መጫወት ለፎክላንድ ደሴቶች የማይችል ይመስላል፡፡ የፎክላንድ ደሴቶች እግርኳስ ሊግ ሊቀመንበር ማይክል ቤትስም የሚጋሩት ይህንን ነው፡፡ ‹‹እንደ አጋጣሚ ሆኖ በደቡብ አሜሪካ ባለው ፖለቲካ ምክንያት ፊፋን መቀላቀል አማራጭ አይደለም››

የፎክላንድ ህልም ግን እስከ አሁን መና አልቀረም፡፡ ሊጉ በአዲስ መስክ ተጀምሮ የተደራጀ እግርኳስ በደሴቶቹ እንደሚኖር ይጠበቃል፡፡ የሊጉ አስተዳደር አርቴፊሻል ሜዳ ለማሰራት ከፎክላንድ መንግሥት ፈቃድ እየተጠባበቀ ነው፡፡ ምክንያቱም አሁን ያሉት ሜዳዎች ለጨዋታ ምቹ አይደሉም፡፡ አስቸጋሪ ንፋስ እና እጅግ ቀዝቃዛው የፈረንጆቹ በጋ የሣር ሜዳዎችን ለረጅም ጊዜ እንዳይቆዩ እያደረጋቸው ነው፡፡

በኤሊዎች ጥላ ከሚጫወት ሊግ፣ በቅርብ ካለ ተጋጣሚያቸው 1600 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ክለብ እና ለሶስት ዓመታት ይፋዊ የውድድር ግጥሚያን እስካላደረገ ክለብ የሚገኙት በእነዚህ የደቡብ አትላንቲክ ደሴቶች ነው፡፡

የኮሜዲያን ልመንህ ታደሰን የአዲስ አበባ ሕይወት የሚያሳይ ፎቶ

$
0
0

ውድ ኢትዮጵያውያን ይህን የመሰለ ታዋቂና ድንቅ አርቲስት በአዲስ አበባ ጎዳና እንዲህ በፎቶ ግራፍ እንደምታዩት ሆኖ ስታዩት ምን እንደሚሰማችሁ ለመገመት አንዳግትም። ዘ-ሐበሻ ይህ አርቲስትን ሕዝብ እንዲረዳውና ወደ ቀድሞ ሕይወቱ እንዲመለስ ሕዝብን ትማጸናለች። እንደምታዩት ኮሜዲያን ልመንህ ታደሰ በጎዳና ላይ እንዲህ ሆኗል። የአርቲስቶቻችን መጨረሻ እንዲህ ሊሆን የቻለባቸው ምክንያትን እርሶ ይዘርዝሩት፤ ሆኖም ግን ከነዲህ ያለው ሕይወቱ ለማውጣት እንረባረብ።
ለረዥም ዓመታት በዋሽንግተን ዲሲ ይኖር የነበረው ይኸው አስቂኝ ኮሜዲያን ወደ ሃገር ቤት ሲሄድ ኢትዮጵያውያኑ ገንዘብ አሰባስበው ወደ ሃገር ቤት ልከውት ነበር፤ እዛም ከሄደ በኋላ ግን ሕይወቱ ይህን መስሏል። ምን ይሻላል?
lemeneh taddesse

ሰማያዊ ህዝቡ በብሔራዊ ደረጃ የሚደረገው ትግል አካል እንዲሆን ጥሪ አቀረበ

$
0
0

ሰማያዊ ፓርቲ ጥቅምት 18/2007 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ የኢትዮጵያ ህዝብ አፋኙን ስርዓት በመቃወምና ከስርዓቱ ጋር ባለመተባበር በብሔራዊ ደረጃ የሚደረገው ትግል አካል እንዲሆን ጥሪ አቀረበ፡፡

ethiopia-blue-party-300x164‹‹የሀገራችን አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሱና እየከፉ የመምጣታቸውን ያህል ገዢው ፓርቲ ቆም ብሎ ከማሰብ ይልቅ ወደ ማይወጣው አዘቅት ውስጥ ሀገሪቷን ጭምር እያንደረደራት ይገኛል›› ያለው የሰማያዊ ፓርቲ መግለጫ ገዥው ፓርቲ ከዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ሂደት ፍፁም በማይጣጣም መልኩ አፋኝ መዋቅሩን በማናለብኝነት እያስፋፋ እንደሚገኝ አብራርቷል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለማናቸውም አስተዳደራዊም ይሁን ፖለቲካዊ ጥያቄዎች ሀይልን በመጠቀም ለመደፍጠጥና ለማጥፋት ቆርጦ በመነሳት ፍፁም አምባገነንነቱን ገፍቶበት የበርካቶች ህይወት እየቀጠፈ እንደሆነ ገልጾአል፡፡

መግለጫው ለስርዓቱ አፋኝነት በምሳሌነት ካነሳቸው መካከል በአለፈው ክረምት ወራት ጀምሮ ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የሚሰጠው የግዳጅ ስልጠና የሚገኝበት ሲሆን በስልጠናው ስነ ምግባር በጎደለው መልኩ የጥላቻ ዘመቻ በማካሄድ የሃሳብ ልዩነትን የማስተናገድ ፍላጎቱ ሙሉ ለሙሉ እንደተዳፈነ ያሳየ ነው ብሎታል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እነዚህን ስልጠናዎች እጅግ በቅርበት ሲከታተላቸው የቆየ መሆኑንና ከጅማሬውም ተቃውሞውን በይፋ መግለጹንም መግለጫው አውስቷል፡፡

ፓርቲው በጋዜጠኞች ላይ የተወሰደው የማሳደድ እርምጃ፣ በነጻው ፕሬስ ላይ የተፈጸመው አፈና የስርዓቱን መበስበስ እና አፋኝ አምባገነንነትን ብቸኛ አማራጭ አድርጎ መቀጠል መምረጡን ግልጽ አመላካች ነው ብሏል፡፡

‹‹እጅግ የከፋውና እየተባባሰ የመጣው ከፍተኛ አደጋ ያዘለ ችግር ያለው አስተዳደራዊ እና ፖለቲካዊ ጥያቄ እያነሱ ያሉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በሀይል ለመግዛት ቆርጦ መነሳቱ ነው›› ያለው መግለጫው በተለይ በኦጋዴን በርካታ ዜጎች በመንግስት ሀይሎች ህይወታቸው መቀጠፉ ሳያንስ ሬሳቸው እንኳን ክብር በሌለው ሁኔታ መሬት ለመሬት እየተጓተተ ባደባባይ ሰብአዊ መብት ሙሉ ለሙሉ መጣሱን አውስቷል፡፡ በተጨማሪም በጋምቤላም የህወሓት ሰዎች መሬት በሕገ-ወጥ መንገድ መቀራመታቸውን የተቃወሙ በርካታ የሰው ህይወት የተቀጠፈበት ሁነት ሀገሪቱ ወደ ከፋ ሁኔታ እያመራች ለመሆኑ አመላካች ነው ሲል ገልጾአል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ገዥው ፓርቲ በህዝብ ላይ የሚፈጽመውን በደል በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን ያስታወቀው መግለጫው ‹‹የሀገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ ከግምት በማስገባት መላው የሀገሪቱ ህዝብ፣ በውጪ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ለሀገር ተቆርቋሪ ተቋማት እንዲሁም በገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ስር ሆናችሁ ለውጥን የምትሹ ወገኖች ሀገራችንን ወደ አደጋ እየወሰዳት ያለውን አፋኝ ስርዓት በቻላችሁት ሁሉ በመቃወምና ከስርዓቱ ጋር ባለመተባበር በብሔራዊ ደረጃ የሚደረገው ትግል አካል እንድትሆኑ›› ሲል ጥሪ አቅርቧል፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም ከዜድቲኢ ጋር የገባውን የ800 ሚሊዮን ዶላር ውል አፈረሰ

$
0
0

-በውሉ መሠረት ፕሮጀክቱ ሳይጀመር ዓመት አልፎታል

ethio_telecom_corp101371252571በአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ውጪ ያለውን የቴሌኮም ማስፋፊያ ፕሮጀክት ለመተግበር የ800 ሚሊዮን ዶላር ኮንትራት የወሰደው የቻይናው ዜድቲኢ ኩባንያ ኮንትራት ተሰረዘ፡፡

እ.ኤ.አ. ኦገስት 18 ቀን 2013 ዜድቲኢ የማስፋፊያ ፕሮጀክቱን ውል ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የተፈራረመ ቢሆንም፣ በውሉ መሠረት በሁለት ዓመታት መጠናቀቅ የነበረበት ፕሮጀክት፣ እስካሁን ባለመጀመሩ ለኮንትራቱ መፍረስ ምክንያት መሆኑን የሪፖርተር ምንጮች ተናግረዋል፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በደብዳቤ ቁጥር ET/CEO/63/2014 በጻፈው የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደገለጸው፣ ዜድቲኢ ፕሮጀክቱን ከማጓተት ተቆጥቦ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ ገብቶ እንዲያጠናቅቅ አሳስቧል፡፡

ዜድቲኢ ለተጻፈለት የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ተዛማጅነት የሌለውና ግራ የሚያጋባ ምላሽ ከመስጠት ባለፈ፣ በገባው የኮንትራት ውል መሠረት ሥራውን ሊጀምር አለመቻሉን፣ ኢትዮ ቴሌኮም በሥራ አስፈጻሚው በአቶ አንዱዓለም አድማሴ ተፈርሞ የወጣው የኮንትራት ውል ማፍረሻ ደብዳቤ ቁጥር ET/CEO/71/2014 ይጠቁማል፡፡

‹‹እልህ አስጨራሽ ከሆነ ድርድር በኋላ የተደረሰበትን ስምምነት በዜድቲኢ ቁርጠኝነት ማጣት ምክንያት ስምምነቱ ጥያቄ ውስጥ ገብቷል፤›› የሚለው በሥራ አስፈጻሚው ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤ፣ የኢትዮጵያ መንግሥትም ሆነ ኢትዮ ቴሌኮም በከፍተኛ ፍላጎት ሲጠብቁት የነበረውን የፕሮጀክቱን መጀመር ተስፋ አስቆራጭ እንዳደረገው ያስረዳል፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም ከዜድቲኢ ጋር በገባው የፕሮጀክት ስምምነት አንቀጾች መሠረት ለመሥራት የመልካም ፍላጎት አለመኖር፣ የኮንትራት ስምምነቱን እንደመጣስ ተደርጎ እንደሚቆጠር በአቶ አንዱዓለም ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤ ያስረዳል፡፡ በተጨማሪም ‹‹ይህ ኮንትራት ማቋረጫ ደብዳቤ ለዜድቲኢ ከደረሰበት ከሰላሳ ቀናት በኋላ ኩባንያው ወደ ሥራ መግባት ካልቻለ በፍቃዱ ኮንትራቱን እንዳቋረጠ ይቆጠራል፤›› ሲል ደብዳቤው ያስጠነቅቃል፡፡

ፕሮጀክቱን ተግባራዊ ለማድረግ ስምምነት ላይ የተደረሰባቸውን አንቀጾች ዜድቲኢ ጠብቆ ካለመጓዙም በተጨማሪ፣ ኩባንያው የኢትዮጵያ መንግሥትና ኢትዮ ቴሌኮም ፕሮጀክቱ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ በሰጡት ትልቅ ትኩረት ላይ ጉዳት ማድረሱም ተጠቁሟል፡፡ በመሆኑም ኢትዮ ቴሌኮም በፕሮጀክቱ አለመጀመርና በተባለው ጊዜ አለመጠናቀቅ ምክንያት የደረሰበትን ጉዳት በሕግ የሚጠይቅ መሆኑ እንዳለ ሆኖ፣ የፕሮጀክት ኮንትራት ስምምነቱ የፈረሰ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ዜድቲኢ በደብዳቤ ቁጥር ዜድቲኢ/CEO/14 0909/01 እ.ኤ.አ. ሴፕቴንበር 9 ቀን 2014 ለኢትዮ ቴሌኮም በጻፈው ምላሽ፣ ፕሮጀክቱን በፍጥነት እንደሚጀምርና በተባለው ጊዜ እንደሚያጠናቅቅ ገልጾ፣ ይህ እንዲሆንም ሁለቱ አካላት ተገናኝተው እንዲወያዩ ጠይቋል፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በጻፈለት ደብዳቤ መሠረት ፕሮጀክቱን የሚያቋርጥ ከሆነ በተናጠል የወሰነው ውሳኔ መሆኑን ለማስታወስ እንደሚወድ ዜድቲኢ በምላሽ ደብዳቤው ገልጿል፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዱዓለም አድማሴ ማብራሪያ እንዲሰጡ ሪፖርተር የተጠየቃቸው ቢሆንም፣ ጉዳዩን ሳያስተባብሉ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡ በተመሳሳይ የዜድቲኢ የሕዝብ ግንኙነት ሠራተኛ ወ/ሮ የምሥራች ብርሃኑ ውሉ አለመቋረጡን ገልጸው፣ ዜድቲኢ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር እስካሁን በድርድር ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዜድቲኢ የመጀመርያውን የአገር አቀፍ ቴሌኮም ማስፋፊያ ፕሮጀክት በ1.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር የሠራ መሆኑ ይታወሳል፡፡ ይህ ኩባንያ ለረዥም ዓመታት ኢንዱስትሪው ውስጥ ቆይታ ቢያደርግም፣ የኢትዮጵያ መንግሥት በቅርቡ ይፋ ያደረገውን የ1.6 ቢሊዮን ዶላር ሁለተኛ ዙር የቴሌኮም ማስፋፊያ ፕሮጀክት ከባላንጣው የቻይናው ኩባንያ፣ ሁዋዌ ጋር እንዲጋራ መገደዱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ በተለይ 4G የተባለውን ዓለም የደረሰበትን የቴሌኮም ቴክኖሎጂ በአዲስ አበባ እንዲዘረጋ የኢትዮጵያ መንግሥት ሁዋዌን መምረጡ ለዜድቲኢ ያልተዋጠለት እንደነበርም ዘግበናል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ዜድቲኢ በሚሳተፍበት የ800 ሚሊዮን ዶላር ማስፋፊያ ፕሮጀከት ላይ የሚያስፈልጉ ማይክሮዌቭ መሣሪያዎችን ከባላንጣው ሁዋዌ ኩባንያ እንዲገዛ መገደዱ ላለመግባባቱና ለፕሮጀክቱ መቋረጥ ምክንያት ሳይሆን እንደማይቀር ምንጮች ገልጸዋል፡፡

በቅርቡም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዜድቲኢ 500 ሚሊዮን ብር የትርፍ ግብር ታከስ አልከፈለም በሚል ውዝግብ ውስጥ መግባቱንና ኢትዮ ቴሌኮምም ምንም ዓይነት ክፍያ እንደማይፈጽም ማስታወቁን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

ባለፉት 23 ዓመታት ውስጥ በልጆቻቸው መታሰር በፅኑ ሃዘን የተወጉትን እናቶች ማሳያ የሆኑት 70 ዓመታት ያለፋቸው የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እናት ተመስገን በተፈረደበት ዕለት የነበሩበትን ሁኔታ የተመስገን ወንድም እንደፃፈው (ኦድዮ)

$
0
0

ከኢሳት ”ስለ ኢትዮጵያ” ከተሰኘው የራድዮ ፕሮግራም የተወሰደ


unnamed
Source:: gudayachn

ዕንባና ጸሎት ያሳደጉት ልጅ (ልቦለድ) – (ከኤፍሬም እሸቴ)

$
0
0

(ደራሲው ኤፍሬም እሸቴ)

(ደራሲው ኤፍሬም እሸቴ)


ይህንን አጭር ልቦለድ ከማንበባችሁ በፊት በቪዲዮ የተቀናበረውን የተመስገን ደሳለኝን ወንድም የታሪኩ ደሳለኝን ጽሑፍ እንታዳምጡ ልጋብዛችሁ። በቪዲዮው ላይ የቀረበው የታሪኩ ጽሑፍ እውነተኛ ታሪክ ሲሆን የእኔይቱ መጣጥፍ ግን ልቦለድ መሆኗን እንድትረዱ በማስጠንቀቅ ወደ ንባቡ ልምራችሁ።
(ቪዲዮው ከዚህ ይገኛል፦ https://www.youtube.com/watch?v=MChq7mR_wCk)
+++
ከዕለታት አንድ ቀን …
እትዬ ሸዋዬ ቤት ውስጥ። ስኒው ተዘርግቶ ቡናው በአንድ ጎን ይቆላል። የተንተረከከው ፍህም ቅላቱ የአፋርን እሳተ ገሞራ የቀለጠ ዐለት ያስታውሳል። በአንድ ጥግ ዳንቴል ለብሳ የተንጠለጠለች ብርቄ ሬዲዮ የምሳ ሰዓት ዜና ታሰማለች። ሕጻናት ውጪ ደጃፉ ላይ ሲጫወቱ የሚያስነሱት አቧራ ገርበብ ብሎ በተከፈተው በር ዘልቆ ይገባል። እንደ ሌላው ጊዜ “እንደው እነዚህ ውጫጮች፤” ብሎ የሚያባርራቸው የለም። ሴቶቹ በሙሉ ጆሯቸውን ከራዲዮኑ ደቅነው በዓይኖቻቸው የልጆቻቸውን ሩጫ ይመለከታሉ። ባሎች ወደ ኦጋዴን ግንባር ከዘመቱ ቆይተዋል። በሰፈሩ ውስጥ ዕድሜያቸው ከገፋ አረጋውያን እና በተለያየ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ከሚሠሩ ሰዎች በስተቀር ደልደል ያለ ወንድ በሰፈሩ ብዙም አይታይም። ወንዱ ሁሉ የናት አገር ጥሪ ብሎ ሚሊሻ ሆኗል።

በርግጥ ሬዲዮኑ ይሸልላል፤ ይፎክራል። ቤት ያሞቃል። ሴቶቹ ግን በዚያ ሁሉ የጀግና ፉከራና ቀረርቶ፣ “ውረድ በለው ግፋ በለው፤ ግደል ተጋደል በአባትህ ወኔ …” መካከል የባሎቻቸው ሕይወት፣ በእነርሱ ላይ እንዳይደርስ የሚፈሩት ነገር ሥጋት …. ያለ አባት ልጅ የማሳደግ ጭንቀት … እየተገለባበጠ ይመጣባቸዋል። ልጆቹ አቧራቸውን ያቦናሉ።
mom and son
+++
ከወር … ከሁለት ወር በኋላ ….
የእትዬ ሸዋዬ ልጆች አሁንም ከደጃፉ እየተሯሯጡ ይጫወታሉ። ግቢው ውስጥ የተተከለው ድንኳን ድብብቆሽ ለመጫወቻ ተመችቷቸዋል። ሰርግ ይሁን መልስ ይሁን ለቅሶ ይሁን ሰንበቴ ለእነርሱ ምኑም ልዩነት አልሰጣቸውም። ሚሊሻ አባታቸው እንደማይመለሱ ገና በቅጡ አልተገለጠላቸውም። ያለ አባት …. በእናት እጅ ማደግ … ያለ ርዳታ … ገና አልገባቸውም።
ቆይቶ … ነፍስ ሲዘሩ፣ ችግር በዚያ በቀዝቃዛ አለንጋው ቤተሰቡን ሲገርፍ … ያኔ ነው የሚገባቸው። ለአሁኑ ልጆች ናቸውና ለለቅሶ የተተከለው ድንኳን እነርሱን ለማጫወት የመጣ ሳይመስላቸው አልቀረም። በልጅነታቸው። ከሌላው ሰው ተለይቶ የእነርሱ ብቻ ቤት ድንኳን ስለተጣለበት ድንኳን የሌላቸውን ጓደኞቻቸውን ለማስቀናት ሞክረዋል።
“እኛ ቤት ድንኳን አ…..ለ፤ ደሞ፤ በ….ቃ” እያሉ ጉራቸውን ነዝተውባቸዋል። ድንኳን የሌላቸውን የመምህር አንበርበር፣ … ደግሞ የመምሬ ከበደ … ወዲያ ማዶ ያሉት ባለሱቁ … የጋሽ አብደላ … ልጆች በሙሉ መጥተው ድንኳኑ ውስጥ ሲጫወቱ ውለዋል። በድንኳኑ ስፋት … እየተደነቁ።

ከዓመት ሁለት ዓመት በኋላ …
ልጆቹ በሙሉ ተሰብስበው ሲጫወቱ ይውሉና … ከዚያ ያ ሁሉ ፍቅራቸው ፈርሶ በዚያው በፍቅሩ መጠን አምርረው ተጣልተው ሰፈር ይረብሻሉ። ከሁሉም ግን የእትዬ ሸዋዬ ልጆች ላይ ነገር ይጠናባቸዋል። ሴት ያሳደገው ልጅ ድሮስ?” ይባላሉ። ሰው ፊት ሰምተው እንዳልሰሙ የሚሆኑት ወ/ሮ ሸዋዬ ዘወር ብለው ድምጽ የሌለው ዕንባ፣ የብቻ ዕንባ ያፈሳሉ። ልጆቻቸው ዕንባቸውን እንዲያዩ አይፈቅዱም።
“ሴት ያሳደጋቸው ልጆች” ሲባሉ ብዙ ጊዜ ሰምተዋል። አማርኛው ግን ገና አልተረዳቸውም። ስድብ መሆኑ እስኪገባቸው ሌሎች ዓመታት መጠበቅ አለባቸው። ገና ልጆች ናቸው። ሚሊሻ አባታቸው ቢኖሩ ይህ ስድብ እንደማይኖርባቸው ለመረዳት ጥቂት ዓመታት ይቀሯቸዋል። በልጅነት ትዝታ የሕልም ያህል ውል ውል የሚሉባቸው የአባታቸው ትዝታ ነፍስ እስኪዘራባቸው ጥቂት ዓመታት መጠበቅ አለባቸው። ጊዜው ሲደርስ “ሴት ያሳደገው ልጅ” ሲባሉ በነብር ቁጣ፣ በአንበሳ ግርማ ከሰው ጋር ለመተናነቅ ለመነሣት ጊዜው አልደረሰም ነበር። ልጆች ናቸዋ።

ከተጨማሪ ዓመታት በኋላ …
ልጆቹ አድገዋል። እርስበርሳቸው መጽናኛቸው የጎረቤት መሳደቢያዋ ቃል ናት፦ “ባክህ እናታችንን እንዳናሰድባት። ሴት ያሳደጋቸው እንዳናስብላት” ይሉ ጀመር። በነበር ቁጣ በአንበሳ ግርማ፤ ነገር ግን ጭምቶች ሆነዋል። እናት የቤቱ አባ ወራም እማ ወራም ናቸው። ልጆች ሰው እንዲሆኑ የታጠቀ ወገባቸውን አልፈቱም። የባላቸውን መርዶ የሰሙ ቀን ቅስማቸው ተሰብሮ ልጆቻቸውን ሳያሳድጉ አልቀሩም። ያኔ የታጠቁትን መቀነት ለማላላት ልጆቻቸው “ቦታ ቦታ እንዲይዙ” ለራሳቸው ምለው ነበር።
ዛሬ ከዓመታት በኋላ ሴት ያሳደጋቸው እነዚያ ልጆች ቦታ ቦታ ሲይዙ የብልግና መነሻ አገሩ አድርጎ ይቆጥራቸው የነበረ ጎረቤት አሁን በአለክብሮት ያያቸዋል። “አይ ወ/ሮ ሸዋ፤ ሴት ሳትሆን እኮ ወንድ ናት። አታዩም ልጆቿን? አንዱም ዩኒቨርሲቲ ያስተምራል፤ አንዱም ጎበዝ ጋዜጠኛ ሆኗል” ይሏቸዋል።

ከሌሎች ዓመታት በኋላ ….
ፍርድ ቤቱ የጋዜጠኛውን ክስ መመልከት ከጀመረ ቆይቷል። በተከሳሽ ሳጥን ውስጥ ቆሞ ባሻገር ወንድሙን እና እናቱን በአንድ ወገን፣ ባለቤቱንና ትንሽ ልጁን በሌላ ወገን ይመለከታል። ሕጻን ልጁ እናቱ ጭን ላይ ተቀምጦ ከኋላው ወንበር ካለ ሰው ጋር ድብብቆሽ ቢጤ ይጫወታል። “አየሁህ …. አየሁህ …..” ይላል።
ወዲያው ድንኳን እቤታቸው ተተክሎ የሰፈር ሕጻናትን ሰብስበው ሲጫወቱ የተደሰቱት ደስታ ትዝ አለው። “ጋዜጠኛ ነኝ፣ ሚሊሻ አይደለሁም። እንደ አባቴ ጦር ሜዳ አልሄድኩም። በርግጥ ፍርድ ቤቱ አሁን ድንኳኔን እየጣለው ነው?” ይላል።
የልጃቸውን ዓይን የተከተሉት ወ/ሮ ሸዋዬ እናቱ እቅፍ ውስጥ የሚጫወተውን ልጅ ሲያዩ የልጃቸው ሐሳብ ምን እንደሆነ እንደተከሰተላቸው ሁሉ ትኩስ ዕንባ ግድቡን ጥሶ ሊፈስ ይታገላቸው ያዘ። ግን ልጆቻቸው ፊት አለማልቀስን ለረዥም ዘመናት ተለማምደውታል። የከባድ ኑሮን ቀንበር አሸንፈው ልጆቻቸውን ዳር አድርሰዋል። ራሳቸውን ጎድተው ልጆቻቸውን ሰው አርገዋል። አሁን ግን የልጃቸውን ልጅ ሲያዩ ጉልበት ከዳቸው። ጋዜጠኛው ልጃቸው የአባት ልቡ ለሕጻን ልጁ ሲንሰፈሰፍ የርሳቸውን ጥንካሬ ናደባቸው። ከፈቃዳቸው ውጪ በየትም ቦታ በየትም ጊዜ እንዳይፈስ ያሰለጠኑት ዕንባቸው ግድቡን ደረመሰ። ወደ ወሕኒ የሚሔደውን ልጃቸውን በዕንባቸው መካከል ያዩታል። በተሰባበረ መስተዋት ውስጥ እንደሚታይ መልክ በተሰባበሩ ዕንባዎችና የዕንባ ዘለላዎች መካከል … በነጠላ ጫማ … “ጺሙ እንዴት አድጓል?” ከወገቡ ጎበጥ ያለ መሰላቸው። መምህሩ ልጃቸው ትከሻቸውን አቅፎ እየመራቸው በተሰባበሩ ዕንባዎች እግራቸውን በዘፈቀደ እየተረገጡ ከፍርድ ቤቱ ወጡ። ሌላ አባት የማያሳድገው ልጅ … የእናቱ ብቻ ዕዳ የሆነ … በኅሊናቸው መጣባቸው። ልጆቻቸውን ሲያሳድጉ ጭንቀታቸውን ወደሚያራግፉበት የእስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ሲደርሱ እንደድሮው ብቻቸውን ብር ብለው አልነበረም። መምህሩ ልጃቸው አሁን እንደደገፋቸው ነው። የተለመደች ታዛቸው ሥር ሆነው “ሰማዕቱ፣ የልጆቼን ነገር አደራ አላልኩህም ነበር? ውለታችንን ረሳኸው?” ሲሉ ልጃቸው እንደሚሰማቸው ትዝም አላላቸው። በዕንባ እና በጸሎት ያደገ ልጅ። እርሱም መሐረሙን አፍንጫው ላይ ከድኖ ድብቅ የወንድ ዕንባውን ማፍሰሱን እሳቸው አላዩም። አንዳንዴ ወንድ ብቻውን አያለቅስም።

(መታሰቢያ፦ ለተመስገን ደሳለኝ፣ የእናታቸውን ታሪክ በግሩም ብዕር ለነገረን ለተመስገን ወንድም ለታሪኩ ደሳለኝ እና ለአረጋዊ እናታቸው።)

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የእስር ቅጣቱን በመቃወም ይግባኝ ሊጠየቅ ነው

$
0
0

በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ህዝብን ለአመፅ በማነሳሳትና ሀሰተኛ መረጃን በመስጠት በሚል ዐቃቤ ሕግ ክስ መስርቶበት የ3 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደበት በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይግባኝ እንደሚጠይቁ ጠበቃው አቶ አመሀ መኮንን አስታወቁ። ጠበቃው አክለውም፤ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን ሕጉ እስከፈቀደው ድረስ ማንኛውንም መድረክ አሟጠን እንጠቀማለን ሲሉ ተናግረዋል። ይግባኝ እንደሚጠይቁ ጠቁመው ያም ሆኖ የተለየ ውጤት ካልተገኘ እስከሰበር ችሎት እንደርሳለን ብለዋል።
በተከሳሹ ላይ ፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ብይን ከሰጠ በኋላ ስለምን የቅጣት ማቅለያ አላቀረባችሁም ተብሎ ከሰንደቅ ጋዜጣ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም፤ በመርህ ደረጃ ጥፋተኛ መባል አልነበረበትም፤ አሁን ጉዳዩ ብዙ ዓመት የመታሰርና ትንሽ ዓመት የመታሰር ብቻ ሳይሆን በዋናነት ለቅጣት ቅነሳ መከራከሪያችን ለህግ ጥፋቱን የማመን ምልክት ስላለው አልፈለግንም።
Temesghen Desalegn (CPJ)cropped
አመፅን ለመቀስቀስ በመሰናዳት ወንጀል ተሳትፎ፤ ሕገ-መንግስቱንና ህገመንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ የሚያነሳሱ ፅሁፎችን በቀድሞዋ ፍትህ ጋዜጣ ላይ ሲያሰፍር ነበር በሚል የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሰረተበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ጥፋተኛ የተባለበት ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ወንጀል ሥር በ3 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ሲል ፍርድ ቤት ባሳለፍነው ሰኞ ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፏል።
ዐቃቤ ሕግ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ሶስት ክሶችን በጋዜጠኛው ላይ አቅርቦ በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች አስረድቷል። ተከሳሹም ከተከሰሰባቸው ወንጀሎች ነፃ ያወጡኛል ያላቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ለፍርድ ቤቱ አቅርቦ የተከራከረ ቢሆንም፤ ችሎቱ የግራ ቀኙን መረጃ መርምሮ ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛ ነህ ብሎት እንደነበር ይታወሳል።
በዐቃቤ ሕግ የክስ ዝርዝር የተጠቀሱት ፍሬ ሀሳቦች መካከል በአንደኛው ክስ ሥር “ሞትን የማይፈሩ ወጣቶች” በሚል ርዕስ ነሐሴ 23 ቀን 2003 ዓ.ም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፃፈው ሀተታ ውስጥ ወጣቶች ለአብዮትና ለለውጥ እንዲነሳሱ በማድረግ፤ በአረቡ አለም ወጣቶች የነበራቸውን ሚና በመጥቀስ አሁን ያለውን ስርዓት ለመቀየር ወጣቶች ለአመፅ እንዲነሳሱ አድርጓል የሚል ነው።
በ2ኛ ክስ ስር የተዘረዘረው ሀሳብ ደግሞ “የሁለተኛ ዜግነት ህይወት በኢትዮጵያ እስከመቼ?” በሚል ርዕስ ሐምሌ 22 ቀን 2003 ዓ.ም በፍትህ ጋዜጣ ባወጣው ሀተታ ስር መንግስት በተለያዩ ክልሎች የጅምላ ጭፍጨፋ ፈፅሟል በማለት የአገሪቱን መንግስት ስም በማጥፋትና በሀሰት ወንጅሏል የሚል ክስ ተመስርቶበታል።
ዐቃቤ ሕግ 3ኛ ክስ አድርጎ ያቀረበው ደግሞ በመጋቢት 7 ቀን 2004 ዓ.ም በታተመችው ፍትህ ጋዜጣ ላይ “ሲኖዶሱና መጅሊሱ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ማጥመቂያ” ሲል ባሰፈረው ፅሁፍ መንግስት የሃይማኖት ተቋማቱን ለፖለቲካዊ ዓላማ እየተጠቀመባቸው ስለመሆኑ በማተት የህዝብን እምነት እንዲሸረሸር አድርጓል ሲል ይከሰዋል።
ተከሳሹ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧቸው በነበሩ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች አማካኝነት በጥቅሉ፤ የጋዜጠኝነት ተግባሩን እየተወጣ በመሆኑንና በዚህም ህገ መንግስቱ የሰጠውን ኀሰብን የመግለፅ ነፃነት ተጠቅሞ ሥራውን ማከናወኑን ባቀረባቸው የመከላከያ ምስክሮች ጭምር አስረድቷል።
ሆኖም የግራ ቀኙን ክርክር ሲመረምር የቆየው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ጥፋተኛ ማለቱን ተከትሎ ባሳለፍነው ሰኞ የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፏል። በዚህም የውሳኔ ንባብ ወቅት ፍርድ ቤቱ እንዳለው፤ ምንም እንኳን ተከሳሹ ጥፋተኛ ቢባልም የቀረቡበት 3 ክሶች በአንድ ሃሳብ ሊጠየቅ የሚገባው ነው በሚል፤ በወንጀል ህጉ የመገፋፋትና ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ተግባር ወንጀል ብቻ ይቀጣ ማለቱን ተከትሎ ምንም አይነት የቅጣት ማቅለያ ባላቀረበው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ የ3 ዓመት ፅኑ እስራት ፈርዶበታል።
በተያያዘም አሳታሚው ማስተዋል የህትመትና ማስታወቂያ ኃ/የተ/የግ ማህበር ላይ ዐቃቤ ሕግ አቅርቦት የነበረው የንብረት ይወርስልኝ ጥያቄን ፍርድ ቤቱ ወደጎን በመተው የ10ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ጥሎበታል።

ምንጭ፦ ሰንደቅ ጋዜጣ


ወያኔ/ህወሓት ያደራጃቸው ምሊሽያዎች በአፋር ነዋሪዎች ላይ ተኩስ ከፈቱ

$
0
0

አኩ ኢብን አፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው፦

ትናንት ማክሰኞ 18/02/2007 በአፋር ክልል በሰሜናዊ ዞን በኮናባ ወረዳ በትግራይ ታጥቂ ሚሊሻዎች በኮናባ ፈራስዳገ ቀበሌ ነዋሪዎች ላይ ጦርነት የከፈቱ ሲሆን ቦታውን በቶክስ እሩምታ ሲያምሱት ማርፈዳቸውን ከቦታው የሚወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ ለጊዜው ከአፋር ነዋሪዎች በኩል የቶክስ ምላሽ አላገኙም! ከቀኑ 8:00 ሰዓት ሲሆን የተጀመረው ይህ ቶክስን ተከትሎ ከኮናባ ወረዳ ብዙ ወጣቶች ተሰብሰበው በፍጥነት ወደ ቦታው የደረሱ ሲሆን በዛን ጊዜ የኔትዎርክ አገልግሎት ወዲያው ተቋርጧል። እስካሁን ከአፋር ነዋሪዎች በኩል የተተኮሰ አንድ ጥይት የለም።
afar
የቦታው ምንጮች አያይዘውም «ይህ ደግሞ የአፋር ወጣቶች ለሰላም ካላቸው ፍላጎት የተነሳ ነው። ነገር ግን አስገዳጅ ነገር ከተፈጠረ የሚደርስባቸውን ጥቃት ለመከላከል ከየቦታው ተሰብስበው ዝግጅት ላይ ናቸው።» ብለዋል። ከኮናባ አንድ ስሙን ሊናገር ያልፈለገ ወጣት እንደነገረኝ «ይሄ በህወሓት ሆን ተበሎ የሚደረግ ትንኮሳ በመሆኑ የአፋር ወጣቶች በበሰለ አስተሳሰብ ለሰላም ያላቸው ፈለጎት በትዕግስት አሳይተዋል።» ብሏል። አያይዞም «ኔትወርክ ራሱ የጠፋው ለሌሎች መረጃ እንዳይደርስና የአፋር ህዝብ እንዳይነሳ በመፍራት ነው» ሲል አክሏል። አሁንም ቦታው ውጥረት እንዳለ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

በዚህ ጉዳይ ላይ የኮናባ ወረዳ የፀጥታ ቢሮ ኃላፊን አስተያየት ለማካተት ያደረኩት ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም።

ቅዱስ ሲኖዶስ ‹‹እነማን ናቸው ከጀርባዎ ያሉት?›› ሲል ፓትርያርኩን ጠየቃቸው

$
0
0

የሐራ ተዋሕዶ ዘገባ

አቡነ ማቲያስ

አቡነ ማቲያስ


አቡነ ማትያስ÷ የሊቃነ ጳጳሳትንና ኤጲስ ቆጶሳትን ተጠሪነት ለፓትርያርኩ በማድረግ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት ሕገ ቤተ ክርስቲያን የመጨረሻው ከፍተኛ ሥልጣን ባለቤት የኾነውን የቅዱስ ሲኖዶሱን የበላይነት በፓትርያርኩ የበላይነት ለመተካት ከምልአተ ጉባኤው ጋራ መሟገታቸውን አጠናክረው ውለዋል፡፡

የቅዱስ ሲኖዶስ አመራር ያላትን ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በፓትርያርኩ ዐምባገነናዊ አመራር ሰጪነት በመርገጥ በስም እንጂ በግብር የሥልጣን ልዕልና የሌለው ሲኖዶስ ለመፍጠር እየተጣጣሩ ነው፡፡

ቤተ ክርስቲያን አንድነትን በሚጠይቅና ከፍተኛ የጥንቃቄ ርምጃዎችን በሚሻ የህልውና ጥያቄ ላይ እንዳለች ያጤኑ የምልአተ ጉባኤው አባላት፣ ፓትርያርኩ የልዩነት ነጥቦችን በማክረር ቤተ ክርስቲያኗን ለኹለት ለመክፈል ላደፈጡ ኃይሎች መሣርያ ሊኾኑ እንደሚችሉ ተገንዝቧል፡፡

ልዩነት በተያዘባቸው የመነጋገርያ ነጥቦች ላይ ከሌላ አካል የተነገራቸው የሚመስለውን ብቻ እየተናገሩ አቋማቸውን ከማክረር በቀር ማብራራትና መተንተን በእጅጉ እንደተሳናቸው የተነገረባቸው ርእሰ መንበሩ፣ ‹‹የነበረው ሕግ እንዳይሠራ የማሻሻያ ረቂቁም እንዳይጸድቅ›› የሚመስል ‹‹ሲኖዶሱን የመበተን›› አዝማሚያ እያሳዩ እንደመጡ ተስተውሏል፡፡

‹‹ቅዱስነትዎ በጣም ተቀይረዋል፤ እነማን ናቸው ከጀርባዎ ያሉት?›› ሲል አጠቃላይ ጉዳዩን በሚገባ በማየት በቤተ ክርስቲያኗ እና በቤተ ክርስቲያኗ ላይ ብቻ አጠንጥኖ መሥራት እንደሚገባ አጽንፆት ሰጥቶበታል፡፡
* * *

እነማን ናቸው ከጀርባዎ ያሉት?

የአማሳኞች ዋነኛ ቡድን መሪ የኾነው ሊቀ ትጉሃን ዘካርያስ ሐዲስ÷ ትላንት ተሲዓት ስብሰባው በድንገት ከተቋረጠ በኋላ ምሽት ላይ ፓትርያርኩን አግኝተዋቸው እንደነበር ተናገረ፡፡ እንደ ሊቀ ትጉሃን ዘካርያስ አነጋገር፣ ፓትርያርኩ ከስብሰባው የወጡት ተብረክርከው ነበር፡፡ ‹‹ለማይኾን ነገር አሠቃያችኁኝ›› ብለው እንዳማረሩም አልሸሸገም፡፡ ‹‹የወሰዱት አቋም ታሪካዊ ነው፤ በተለይ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ›› በማለት ‹‹ሲያክሟቸው እንዳመሹ›› የጠቀሰው ሊቀ ትጉሃን ዘካርያስ፣ መንግሥት የማኅበሩ ገንዘብ ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ማእከላዊ ካዝና መግባቱን እንደሚፈልግና በዚኽ ጉዳይ የጀመሩትን ጠንክረው እንዲገፉበት አበረታተናቸው ደስ ተሰኝተዋል ብሏል፡፡

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን የፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት በማድረግም በቅስቀሳቸው ሆ ብለው አልነሣ ያሏቸውንና በሸዋ ጳጳሳት በተለይ በአቡነ ማቴዎስ የሚመኩትን የሸዋ የአድባራት አለቆች ከአዲስ አበባ ለማንኮታኮት ማቀዳቸውን ገልጧል፡፡ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን የሸዋ ስብስብ ነው፤ ነገ ጠዋት የሸዋ አለቃ ሲጠፋ የምትገቡበት እናንተ ናችኹ፡፡››

ሚኒስትሮች ባልተወራረደ የመንግስት ገንዘብ ጉዳይ ላይ ጎራ ለይተው ተከራከሩ

$
0
0

ኢሳት ዜና :-የፌደራል ዋና ኦዲተር፣ አባካኝ የመንግስት ተቋማት በሚል ለጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት እና ለተወካዮች ም/ክር ቤት አፈ ጉባኤ ያቀረበው ሪፖርት ለህዝብ ይፋ ይሁን አይሁን የሚለው ጉዳይ ሚኒስትሮችን አወዛግቧል።

943አቶ አባዱላ ገመዳ፣ አቶ ደመቀ መኮንን፣ አቶ አዲሱ ለገሰና አቶ ጸጋየ በርሄ፣ የፌደራል ኦዲተሩ ሪፖርት ለህዝብ በፍጹም ሪፖርት መደረግ የለበትም ብለው ሲከራከሩ፣ የመንግስት ጉዳዮች ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈርያት ከማል፡ ለህዝቡ ይፋ በሆነ መልኩ የማሳወቅ እርምጃ መውሰድ ይገባል የሚል አቋም አንጸባርቀዋል። አቶ በረከት ስምኦንና ጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ ለዘብተኛ የሆነ አስተያየት በመስጠት አቃም ለመያዝ በመቸገራቸው ጉዳዩ እልባት ሊያገኝ አልቻለም።

በውይይቱ ላይ የጥሬ ገንዘብ ሂሳብ ከመዝገብ /ሌጀር / ጋር የማይመሳከር መሆኑ፣ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ በቆጠራ ከተገኘው ጥሬ ገንዘብ በማነስ ሪፖርት የተደረገ መሆኑ፣ የጥሬ ገንዘብ ቆጠራ የማያደርጉ ወይም የጥሬ ገንዘብ ቆጠራ አድርገናል ቢሉም ማስረጀ ያላቀረቡ መሆኑ፣ በባንክ ሂሣብ ገቢ ለሆኑ ሂሣቦች የገቢ ደረሰኝ ያለማዘጋጀትና ያለመመዝገቡ፤ የባንክ ሂሳብ ማስታረቂያ የማያዘጋጁ መሆኑ፤በበጀት ዓመቱ መጨረሻ በባንክ ሂሳብ መግለጫ ዜሮ ከወጪ ቀሪ እየታየ አላግባብ በባንክ ያለ ገንዘብ ተብሎ ሪፖርት የሚደረግ መሆኑ፣ በወጭ ምንዛሬ ባንክ ያለ ገንዘብ /41ዐ2/ ተብሎ ሪፖርት የተደረገውን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ የባንክ ሂሳብ መግለጫ ያልቀረበበት ሆኖ መገኘቱ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ድክመቶች ተብለው ተነስተዋል።

ስለመንግሥት ሂሳብ አያያዝ የወጣው ደንብ የደመወዝ ሰነድ ሂሳብ የወሩ ደመወዝ በሚከፈልበት ጊዜ የሥራ ማስኬጃ የሚመለከተው ደግሞ በተለይ የግዥ ሰነድ ከተሰጠበት ቀን አንስቶ በሰባት የሥራ ቀናት ውሰጥ እንዲጠናቀቅ ቢያዝም፣ በኦዲተር መስሪያ ቤቱ ከተመረመሩ መ/ቤቶች ውስጥ በ43 የፌደራል መንግስት መ/ቤቶች ብር 7 ቢሊዮን 99 ሚሊዮን 495 ሺ 265 ብር ከ01 ሳንቲም የሰነድ ሂሳብ በደንቡ መሠረት ሳይወራረድ ተገኝቷል፡፡

ሂሳባቸውን ባለማወራረድ ከፍተኛውን ድርሻ ከያዙት መስሪያ ቤቶች መካከል የትምህርት ሚኒስቴር ብር ከ451 ሚሉዮን ብር በላይ ፣ግብርና ቴክኒክ ሙያና ትምህርት ስልጠና ብር 232 ሚሊዬን ፣የመከላከያ ሚ/ር ብር 228 ሚሊዬን ፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ብር 225 ሚሊዬን፣ ጎንደር ዩንቨርስቲ 89 ሚሊዬን ፣መቀሌ ዩንቨርስቲ ብር 36 ሚሉዬን ፣ግብርናና ገጠር ልማት ሚ/ር የምግብ ዋስትና ዳይሬክቶሬት ብር 23 ሚሊዬን እና ማዕከላዊ ስታስቲክስ ብር 23 ሚሊዩን ብር ይገኙበታል ።

ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተወጣጣ ኮሚቲ ተቋቁሞ ባደረገው ጥረት የብር 767 ሚሊዮን 425 ሲ ከ 04 ሳንቲም ሰነድ የሚወራረድበትን መንገድ ለማመቻቸት እየሰራ መሆኑ ቢገለጽም ፣ በሌሎች መስሪያ ቤቶች ስላለው ሁኔታ በዝርዝር አልታወቀም።

ውዝፍ ሰነዱን በወቅቱ አለማወራረድ ለመንግስት ገንዘብ መጥፋት በር የሚከፍት ስለሆነ በአስቸኳይ መወራረድ እንዳለበት ፣ ለረጅም ዓመታት ሳይሰበሰቡ የተገኙት ሂሳቦች እንዲወራረዱ አስፈላጊው ክትትል እንዲደረግ፤ ሊሰበሰቡ በማይችሉት ላይ በመንግስት መመሪያ መሠረት ከመዝገብ እንዲሰረዙ እንዲደረግ ኦዲተር መስሪያ ቤቱ አስተያየቱን አቅርቧል።

በገቢ ግብር፣ቀረጥና ታክስ እንዲሁም በሌሎች ገቢ መሰብሰብ በሚፈቅዱ አዋጆች መሠረት የመንግስትን ገቢ የሰበሰቡ መሆኑን ለማረጋገጥ ኦዲት ሲደረግ ደግሞ፣ በ1ዐ መ/ቤቶች ውስጥ 5 ቢሊዮን 492 ሚሊዮን 319 ሺ 53 ብር በተለያዩ ምክንያቶች ሳይሰበሰብ ተገኝቷል፡፡

ሂሳቡ ሳይሰበሰብ ከቀረበባቸው ምክንያቶች መካከል በትክክለኛው የታሪፍ ቁጥር (Harmonized System code) እና(custom procedure code) ባለለመደባቸው ያልታሰበሰበ ቀረጥና ታክስ ፣የመነሻ ዋጋ የተወሰነላቸው ዕቃዎች በመነሻ ዋጋው መሰረት ያልተሰተናገዱ ድርጅቶች መገኘታቸው ፣በማነፃፀሪያ ዋጋ መሰረት ቀረጥና ታክስ ባለመሰራቱ እና መ/ቤቶች ከሚፈፀሙት ግዥ ላይ ቀንሰው ማስቀረት የሚገባቸው ግብር ( Withholding tax) ፤የተጨማሪ እሴት ታክስ እና ሥራ ግብር ሳይቀነሱ መቅረታቸው የሚሉት በኦዲተሩ ሪፖርት ተመልክተዋል።
ስለሁኔታው ትኩረት ተሰጥቶት የመንግስት ህግና ደንብ ተከብሮ እንዲሰራ ፣ ያልተሰበሰበውም ገቢ እንዲሰበሰብ መስሪያ ቤቱ አሳስቧል።

በገቢ ሰብሳቢ መ/ቤቶችና አገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች በወጣው ህግና ደንብ መሠረት የመንግስት ገቢ በአግባቡ መሠብሰባቸውን ለማረጋገጥ ኦዲት ሲደረግ ደግሞ በገቢዎች ጉምሩክ ባለስልጣን ስር ባሉ ሶስት ቅርጫፍ ጽ/ቤቶች ከወለድና ቅጣት መሰብሰብ የሚገባው ብር 323 ሚሊዮን 794 ሺ 818 ብር ከ43 ሳንቲም፤ በጉምሩክ የአዳማ ቅ/ጽ/ቤት ብር 78 ሚሊዮን 973 ሺ 321 ከ94 ሳንቲም የአዲስ አበባ ኤርፖርት ቅ/ጽ/ቤት ሊሰበሰብ የሚገባው ብር 5 ቢሊዮን 934 ሺ 794 ከ47 ሳንቲም ከ6 ወር በላይ የቆየ ውዝፍ ሂሳብ የተገኘ ሲሆን ፤ የአዲስ አበባ የወጪ ዕቃዎች ማስተናገጃ ቅ/ጽ/ቤት የተወሰነላቸው የጊዜ ገደብ ጠብቀው ባለመጓጓዛቸው ተገቢ ቅጣት ከተወሰነላቸው ሾፌሮች እና ወኪሎች ያልተሰበሰበ ብር 30 ሺ 000.00 በድምሩ ር 394 ሚሊዮን 495 ሺ 607 ከ69 ሳንቲም በወቅቱ ያልተሰበሰበ ውዝፍ ገቢ ተገኝቷል፡፡፡

የተሰበሰበውን ገቢ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ኦዲት ሲደረግ ፣በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ስር ባሉ ሶስት ቅርጫፍ ጽ/ቤቶችና በሌሎች ሶስት መ/ቤቶች በድምሩ ብር 69 ሚሊዮን 753 ሺ 608 ከ97 ሳንቲም የገቢ ደረሰኝ እና የግብር ማሳወቂያ በፋይሉ ጋር ተያይዞ ባለመገኘቱ ምክንያት ፤ከማን እንደተሰበሰበ ሳይገለጽ በኮድ በመሰብሰቡ የተሰበሰበው ገቢ መሰብሰብ በሚገባው ልክ መሆኑን ለማረጋገጥ ባለመቻሉ የተሰበሰበው ገቢ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ሳይቻል ቀርቷል፡፡

በበጀት ዓመቱ የተሰበሰበው ገቢ በትክክል ተመዝግቦና በሂሳብ ሪፖርታቸው ተካቶ ለገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር መቅረቡን ለማረጋገጥ ኦደት ሲደረግ ፤ 9 መ/ቤቶች ባቀረቡት ዓመታም የገቢ ሂሳብ ሪፖርት ውሰጥ ብር 659 ሚሊዮን 51 ሺ ሳይካተት ተገኝታል፡፡

ይህ ሪፖርት ለህዝብ ይፋ ቢሆን፣ ለመንግስት ከፍተኛ ኪሳራ እንደሚያመጣ የተከራከሩት የእነ አባዱላ ቡድን፣ ሪፖርቱ በታሹ ቃሎች እንዲቀርብ ይፈልጋል። ወ/ሮ ሙፈሪያ ደግሞ በመስሪያ ቤቶች ላይ እርምጃ መውሰድ ካልተጀመረ ችግሩ የከፋ እንደሚሆን ተከራክረዋል። አቶ በረከትና አቶ ሃይለማርያም አቋም ለመያዝ ተቸግረው ታይተዋል።

አቶ መለስ ዜናዊ ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ሪፖርት ሲቀርብላቸው ሪፖርቱ እንዲጣራ ከመጠየቅ ይልቅ፣ በጄኔራል ኦዲተሩ ላይ እርምጃ መውሰዳቸው የአንድ ወቅት መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። መንግስት ተገቢውን ቁጥጥር ባለማድረጉ በእያመቱ በመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚታየው የገንዘብ ጉድለትና ብክነት እየጨመረ ሲሆን፣ በአገሪቱ ለሚታየው ከፍተኛ ሙስናም አስተዋጽኦ እያደረገ ነው።

ገዢው ፓርቲ ንፁሀን የፖለቲካ አመራሮች ጋዜጠኞችና ጦማሪያንን በደል ለማሳጠር እንዲቻል አንድነት ፓርቲ መላው ኢትዮጵያ ህዝብ እንዲነሳ ጥሪ አቀረበ

$
0
0

1920081_720292178055719_7443225194049807735_nአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ዛሬ በጽ/ቤቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ፡፡
ፓርቲው በሰጠው መግለጫ ገዢው ፓርቲ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለሥርዓቱ ያሰጉኛል የሚላቸውን ንፁሀን የፖለቲካ አመራሮች፣ ጋዜጠኞችና ጦማሪያንን በህገ ወጥ መንገድ ክስ መስርቶ ማሰሩ ሳያንስ ኢሰብአዊ በሆነ መንገድ በእስር ቤት እያሰቃያቸው ይገኛል፡፡ ፓርቲው ይህንን የበደል ዘመን ለማሳጠር እንዲቻል መላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲነሳ ጥሪ እናቀርባለን ብሏል፡፡

 

 

997075_720293321388938_6063689389032781179_n

1920081_720292178055719_7443225194049807735_n

10392406_720292508055686_6642885533482986101_n 10521791_720292608055676_1244395237942149339_n

 

አይቴ ብሔሩ ለኦሮሞ፤ የኦሮሞ አገሩ እንግዲህስ የት ነው?

$
0
0

(ከኤፍሬም እሸቴ)

ገና ሃይ ስኩል ተማሪ ነኝ። የትምህርት ጥማቴ ገና ያልወጣልኝ። ተስፋዬን በደብተሬ ቅጠሎች መካከል አቅፌ የምዞር። ሰው ለመሆን የምማር። ተስፋዬን ከመናገሻ ተራራ ጀርባ የተሰቀሉ ይመስለኝ ነበር። ጠዋት ከእንቅልፌ ስነሳ፣ ከተራራው ገመገም ጀርባ የምትወጣው ፀሐይ ተስፋዬ በካዝና ከተቀመጠበት አገር የምትመጣ እንደሆነ ሁሉ ሙቀቷ ብርዴን፣ ጨረሯ ችግሬን ያስረሱኝ ነበር።
Because_I_am_Oromo_

ገና ወፎች ጭውጭው ሲሉ የገነት ጦር ት/ቤት ሰልጣኝ ካዴቶች በዋናው አስፓልት ላይ የዕለቱን ስፖርት ለመከወን በሰልፍ ሲሮጡ፣ ከስከስ ጫማቸው ከአስፓልቱ ጋር ሲገናኝ የሚፈጥረው ድምጽ ሰፈራችንን ከእንቅልፍ ድብርቱ ያባንነዋል። ወደ ላይ እየሮጡ ሲሔዱ ሰምተናቸው ከ30 ደቂቃ በኋላ እየሮጡ ይመለሳሉ። ዋናውን ስፖርት ለመሥራት እየተሟሟቁ መሆን አለበት። ዋናውማ ካምፓቸው ውስጥ ነው። ከሰኞ እስከ አርብ ሁሌም ሲሮጡ ይሰማል። ወጣት የአገሬ ልጆች። ቆይተው “ተመረቁ” ይባልና ሰሜን ጦር ግንባር … ኤርትራ …. ትግራይ ….። ከዚያ መርዶ …።

አንዱ ቀን ጠዋት ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ የካዴቶቹ ከስክስ ጫማና ሩጫው አይደለም። ከዘራውን ተመርኩዞ የሚያዘግም ጠይም መልከ መልካም ሽማግሌ እንጂ። ደብዘዝ ወዳለችው ቤት ሲገባ ብርሃን በቅጡ የምታገኝበት መስኮት ላልነበራት ክፍል የእርሱ ፈገግታ ቤቱን ሲሞላው ይታወቀኛል።

እንደ ሁሎቹም የእናቴ ዘመዶች መልከ መልካም ፊቱ፣ በእርግና ያልደከመ ገጹ፣ ፈገግታ ያልተለየው ዓይኑ፣ ሰልካካ አፍንጫው …. ከዕድሜው አብዛኛውን በስደትና በእስር ያሳለፈ አይመስልም። እናቴ “ጋሽ ኢጀታ” … ብላ ስማው … እኛም የማናውቀውን … በዝና ብቻ ስለርሱ የጠገብነውን አረጋዊ ሰላምታ ሰጥተን … “ቁጭ በል ቁጭ በል” ብላው አረፍ አለ። ለመቀመጥ ወገቡን ካጠፈበት እስከተቀመጠበት ባለችው ቅጽበት አረጋዊው ጋሽ ኢጀታ ከእርጅናው በላይ በሽታ ውስጡን እንዳደከመው ያስታውቃል።

በዚያች በምታምር ከዘራው መሬቱን እየቆረቆረ ከእናቴ ጋር ብዙ ብዙ ተጫወቱ። ዓይኑን ግን ከእኛ ከወጣቶቹ ላይ አልነቀለም። አንዴም በአማርኛ አንዴም በኦሮምኛ ሲያወራ እናቴ ግማሹ አማርኛ ግማሹ ኦሮምኛ በሆነ ኦሮአማርኛ ስትመልስለት እየሳቀም ራሱን እየነቀነቀም ያዳምጣታል።

የሸዋ ሰው ሁሉ ነገሩ ቅይጥ ነው። አባቱ አማራ፣ እናቱ ኦሮሞ፤ ዘመዶቹ ጉራጌዎች፣ ጎረቤቶቹ የኤርትራ ልጆች፣ ገበያ ሽንኩርት የሚገዛው ከወላይታዎች፣ ወታደሮቹ የትግራይ ሰዎች፣ አስተማሪዎቹ የሲዳሞ ልጆች …. ሆለታ እንዲህ ቅይጥይጥ ያለች ከአዲስ አበባ ውጪ ያለች መርካቶ ናት። የሸዋ ኦሮምኛው እንደዚያው ቅይጥይጥ ያለ ነውና ጋሽ ኢጀታ እየሳቀ የሚሰማት ለምን እንደሆነ የገባኝ ኋላ ነው።
“ሸገር ባኔ፤ ሸገር ወጥተን
ጠጂ ጠጣኔ፤ ጠጅ ጠጥተን
ዱላ’ዻን ተደባደብኔ፤ በዱላ ተደባድበን” እያለ ይቀልዳል አንድ ወዳጄ። ከዚህ ንግግር ውስጥ “ባኔ፤ ሸገር፣ ‘ዻን” የሚሉት ቅንጣቶች ካልሆኑ በሙሉ ኦሮምኛ አይደለም።

“ደህና ነኝ፤ ይቺ ሪኽ አስቸገረችኝ እንጂ። አሁን እግሬንም እንደልብ ማዘዝ እያቃተኝ ነው። ያመኛል ሲነሳብኝ” ብሎ መለሰላት፤ “ጤናህ እንዴት ነው ጋሽ ኢጀታ?” ላለችው ለእናቴ ጥያቄ።

እኔ ደግሞ ዝም ብዬ አስባለሁ። ከእስር የወጣ ሰው እንዲህ ፈገግታ በፈገግታ ይሆናል? እያልኩ። ስለበሽታው እያወራ እንዴት ግንባሩ ላይ የስቃይ ምልክት ሳይሳልበት ቀረ? እያልኩ።
Oromo
ጋሽ ኢጀታ ከእናቴ ጋር ከተጫወተበት ጊዜ ይልቅ ከእኛ ከልጆቹ ጋር ያወራበት ይበልጣል። ምናልባት በዚህች ምድር ላይ የሚቆይባቸውን የመጨረሻ ወራት የራሱን ልጅነት እያስታወሰ፣ ደግሞም የወደፊት የአገሩን ተስፋ በእኛ ውስጥ እያየ ይሆናል። ሰው ከአገሩ ሲወጣ ወይም በእርግናው ወራት ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ የተወለደበት መንደር በሙሉ እጅጉን ይናፍቁት ይሆናል።
ለምን እንደታሰረ፣ ለምን በስደት ሱዳን አገር እንደኖረ በቀጥታ ባይነግረንም ቤት ውስጥ ሲወራ ከሰማነው ጋር ከእርሱም የቀራረምናትን ይዘን መጠነኛ ግንዛቤ አለን። በሜጫና ቱለማ መረዳጃ ማኅበር ምክንያት በንጉሱ ዘመን አገሩን ጥሎ ሱዳን ገባ። አብዮት አብዮት ሲባል ተመለሰ። እንደገና እነ ንጉሥ መንግሥቱ ኃ/ማርያም አሰሩት። ከእስር ከወጣ ብዙም ሳይቆይ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ይህንን ሁሉ የመከራ ቀንበር የተሸከመ ሰው በዘመኑ መጨረሻ ሳገኘው ፊቱ ላይ ፈገግታውን እንጂ ምሬቱን አላየሁም። “ከኦሮምኛ ውጪ አልናገርም” የሚል የቂመኝነት እና አንድን ወገን የመጥላት ነገር አላየሁበትም። “መሞቴ ካልቀረ እስቲ በደሌን ልናገር” ብሎ ለእናቴም ሆነ ገና በማደግ ላይ ለነበርነው ለእኛም በልባችን ቂም የሚያስቋጥር መልእክት አልተናገረም። የእርሱ ዘመድ በመሆናቸው በሌሉበት መከራ የተቀበሉ ዘመዶቹንም እያነሣ “ግፋ በለው፤ ሒድ በለው” አላለም።

“ምክንያቱም ኦሮሞ ስለሆንኩ/ ‪Because I am Oromo‬” የሚለው የአምንስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት ሲወጣና በኦሮሞዎች ላይ በሕወሐት አስተዳደር እየደረሰ ያለውን ነገር ስመለከት ወደ ውስጡ ገብቼ በጥልቅ ሳላየው ይህ አጭር ሐረግ ኅሊናዬን ሰቅዞ ያዘው። ስምህ ወይም የምትናገረው ቋንቋ ለዚህ ሁሉ መከራ ይዳርግሃል ማለት ነው። አሁንማ መታወቂያህ ላይ ሳይቀር በግድ የምትለጥፈው የብሔረሰብ ስም ሊያስገድልህ ወይም ሊያስሾምህ ይችላል። በዚህ ዘመን ጋሽ ኢጀታ ቢኖር ኖሮ ይህንን መከራ ድጋሚ እንደሚቀበል አሰብኩ። ኢጀታ ስለሆነ ብቻ።

ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በብሔረሰቡ ምክንያት፣ አማር በመሆኑ ብቻ የተፈናቀለውን ወገን አስቤ “አይቴ ብሔሩ ለአማራ፤ የአማራ አገሩ የት ነው? ኢትዮጵያ አይደለምን?” (http://www.adebabay.com/2013/04/blog-post.html) ብዬ የጻፍኩትን ተጠየቃዊ ጽሑፍ አስታወስኩ። እዚያው ላይ “አይቴ ብሔሩ ለኦሮሞ” ብዬ መጨመር አለብኝ።
ኢትዮጵያ አሳዘነችኝ። የአገር ዋርካ ኦሮሞ፣ ትልቁ ኦሮሞ፣ ኦሮሞ ሰፊው፣ ኦሮሞ ሆደ ሰፊው ሲያለቅስ … እናም የሚመጣው ሲታሰበኝ … ኢትዮጵያ አሳዘነችኝ።

ኢትዮጵያ አሳዘነችኝ!!!!! ልጆቿ በየስማቸውና በየቋንቋቸው በየተራ መከራ ሲቀበሉ። ሳይረዳዱ … እየተያዩ በየተራ ሲያልቁ። የሰላሌው አያቴ ከአባይ ማዶ ሚስት አገባና አባቴን አስገኙ። ከመንዝ የመጡት ቅድመ አያቴ እምዬ የሜታውን ወጣት አገቡና እናቴንና ዘመዶቿን አስገኙ። ዛሬ ግን የእምዬ ወገኖች ከዚያ ማዶ፣ የአባይ ማዶዋ አያቴ ወገኖች ከዚያ ማዶ … የሜታና የሰላሌ ዘመዶቼ ወገኖች ከዚያ ማዶ … እኛ ከእነርሱ የተፈጠርነው ከተሜዎች ከዚህ ማዶ … የተለያየን ሆንን ማለት ነው? መታወቂያችን የሚያሳየው አንድ መሆናችንን ሳይሆን የተለያየን መሆናችንን ነው።
++
(ማስታወሻ፦ በዘር እና ወንዝ በሽታ ልትከሰኝ የምትፈልግ ካለህ ጊዜህን አታጥፋ። የሚሆነውን ነገር ለማየት ዓይንህን ጨፍነህ ቃላት ለመሰንጠቅ አትድከም። ከምታለቅሰው እናት፣ ከሚሞተው ወጣት፣ ያለ ወላጅ ከሚቀረው ሕጻን ልጅ ይልቅ፣ ተደላድለህ የተኛህበት ሕይወትህ፣ ምንም ነገር መስማት የማይፈልገው ዕዝነ ልቡናህ እንዳይረበሽ “አትጩኹብኝ፣ አትረብሹኝ እስቲ” የምትለውን … አልሰማህም።)

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live