Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ወያኔ ሲያስር አሜን….ሲገድልም አሜን

$
0
0

ነሚያህ

tplfብዕር የያዘ ማንም ሰዉ በዘመናችን ደግሞ የኮምፒተር መክተቢያ ፊቱ ላይ የደቀነ ሁሉ ከሱ ዉጭ ያለዉን ማንንም ሰዉ “ሌባ”፤ “ባንዳ” ወይም “ከሃዲ” እያለ እንዳሰኘዉ መጻፍ ይችላል። በተለይ በእንደኛ አይነቱ ሀላፊነትም ተጠያቂነትም በሌለበት ህብረተሰብ ዉስጥ ደግሞ የጓደኛዉ ሀሳብ ያልተስማማዉ ሁሉ እየተነሳ የገዛ ጓደኛዉን ባንዳና ከሃዲ አድርጎ ስለሚስለዉ የላይ የላዩን ብቻ ለሚመለከት ሰዉ አገራችን በባንዳና በአገር ወዳድ መሳ ለመሳ ለሁለት የተከፈለች ትመስላለች።  እግዝአብሄር ይመሰገን እዉነቱ ግን ከዚህ እጅግ በጣም የተለየ ነዉ። ርዕሴን የጀመርኩት አሜን ብዬ ነዉና እስኪ አንባቢዉ አንተም አሜን በል። ባንዳነትና ከሃዲነት ኃብታምና በእድገት ወደፊት የገፉ አገሮችን እየዘለለ ደሃና ኋላ ቀር አገሮችን ብቻ የሚጠናወት ተራ በሽታ አይደለም። ብዙዎቻችን አምባገነን መሪዎቻችንን ሸሽተን የተጠለልንባት አገር አሜሪካ እነ ሄንሪ ቤስትንና ጆን ብራዉንን የመሳሰሉ ከሃዲዎችን እንዳበቀለች ሁሉ ኢትዮጵያችንም ትናንት እነ ኃ/ሥላሤ ጉግሳን ዛሬ ደግሞ የኃ/ሥላሤ ጉግሳ የልጅ ልጆች የሆኑትን እነ መለስ ዜናዊን፤ አባይ ፀሐዬንና ሰብሃት ነጋን የመሳሰሉ የለየላቸዉ ከሀዲዎችን አፍርታለች። በነገራችን ላይ ሙስሊሙ በዱአዉ፤ ክርስቲያኑ በፀሎት፤ ጠቢብ በጥበቡ ፤ፀሐፊ በምናቡ የባንዳዉንና የከሃዲዉን ብዛት ለመቀነስ ካልተባበሩ በቀር “ወላድ በድባብ ትሂድ” ብለን ባንመርቃቸዉም የባንዳ አባትና አናት አስካሉ ድረስ ባንዳም መወለዱ አይቀርም።

ደጅአዝማች ኃ/ሥላሤ ጉግሳ ማንም ሳያስገድደዉ ወድዶና ፈቅዶ ለወራሪዉ የጣሊያን ጦር ካደረ በኋላ ከጄኔራል ደቦኖ ጋር ሆኖ እናት አገሩን ኢትዮጵያን ወግቷል። ጣሊያኖች ኃ/ሥላሤ ጉግሳ ከነተከታዮቹ ከጎናቸዉ ተሰልፎ አገሩን ሲወጋ ያደረጉት የመጀመሪያዉ ነገር ይህ ከሃዲ ሰዉ ከጎናቸዉ መሰለፉን የሚያሳዩ ፎቶግራፎች ለዓለም ህዝብ ማሰራጨት ነበር። ታሪክ እራሱን ይደግማል ሲባል አይኑ አላይ እያለዉ በጆሮዉ ብቻ ለሰማ ሰዉ ዛሬ ማረጋገጫዉ እነሆ በግልጽ ቀርቦለታል። ትናንት ማክሰኞ መሰከረም 27 ቀን የወያኔ ቴሌቭዥንና ሬድዮ ኢትዮጵያ ዉስጥ በጋዜጠኞች ላይ የሚፈፀመዉን እስርና ስደት፤ ወያኔ በወገኖቻቸን ላይ የሚፈጽመዉን የዕለት ከዕለት ሰቆቃና እንዲሁም በቅርቡ አምቦና ኦጋዴን ዉስጥ የተካሄዱትን የጅምላ ግድያዎች የሚደግፉ የዚህ ዘመን ኃ/ሥላሤ ጉግሳዎች ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ያካሄዱትን የክህደት ሰለማዊ ሠልፍ በተደጋጋሚ ለህዝብ አቅርበዋል። እነዚህ ትናንት ክቡር ባንዲራችን በአለባሌ ሰዉ አንደበት “ጨርቅ” ተብላ ስትሰደብ ከተሳዳቢዉ ሰዉ ጎን ቆመዉ የሳቁና የተሳለቁ ከሃዲ ሆድ አምላኪዎች ዛሬ “ባንዲራችን ተደፈረ” ብለዉ የአዞ እምባ ያነቡብናል። የትኛዉ ባንዲራ?  ለመሆኑ እነዚህ “እናቴን ያገባ ሁሉ አባቴ ነዉ” ባዮች ጀግናዉ ዘርዐይ ደረስ ጣሊያኖችን በራሳቸዉ አደባባዮች አንገታቸዉን በጎራዴ የቀላዉ ለዬትኛዉ ባንዲራ እንደሆነ ያዉቃሉ? እነ አብዲሳ አጋ፤ በላይ ዘለቀ፤ ባልቻ አባ ነብሶና እልፍ  አዕላፋት የኢትዮጵያ ልጆች ምትክ የሌላትን ህይወታቸዉን የሰጡት ለዬትኛዉ ባንዲራ አንደሆነ ያዉቃሉ?

እነዚህ ወያኔ አዲስ አበባ ዉስጥ የገዛ ወገኖቻዉን ሲያስርና ሲገድል አሜን ብለዉ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ሠላማዊ ሠልፍ የሚወጡ የለየላቸዉ ከሃዲዎች ባንዲራ አዲስ መንግስት በመጣ ቁጥር እንደ ፖሊሲና እንደ ካቢኔ ሚኒስቴር የማይቀያየር ቋሚ የአገር ማንነትና የትዉልድ ትስስር መታወቂያ መሆኑን ሊገነዙ ይገባል። ባንዲራ ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ሊቀየር ይችላል ብለን ብናስብ እንኳን ምን አይነት ሰዎች ብንሆን ነዉ ባንዲራን የመሰለ ህዝብና አገር ማስተሳሰሪያ ማተብ ኢትዮጵያንና ታሪኳን ከልቡ ለሚጠላዉ መለስ ዜናዊና   የትግራይ ሪፓብሊክ ካላቋቋምኩ ብሎ ይታገል ለነበረዉ ለከሃዲዉ  ስብሀት ነጋ የምንተዉላቸዉ? ደግሞም  እነዚህ ምናምንቴዎች አንደሚሉት ባንዲራችን ላይ ባዕድ አካል ሆኖ የተለጠፈዉና የኢትዮጵያ ህዝብ በተለምዶ “ባላ አምባሻዉ” እያለ የሚጠራዉ የወያኔ ጨርቅ እዉነትም ኢትዮጵያ ዉስጥ የብሄር ብሄረሰቦችን እኩልነት አረጋግጦ ቢሆን ኖሮ ዛሬ አገራችን  በየቀኑ ብሄር ብሄረሰቦች ዉጣልኝ አልወጣም እየተባባሉ የሚተላለቁባት አገር አትሆንም ነበር።  አባቶቻችን የሞቱት ለአረንጓዴ፤ ብጫና ቀይ ባንዲራ ነዉ፤ እኛም ዛሬ በየተሰደድንበት አገር አገሬን እያሰኘ የሚያስጮኸን ይሄዉ አረንጓዴ፤ ብጫ ቀይ ባንዲራችን ነዉ። አገር ቤት ያለዉ ኢትዮጵያዊም አንዱን “ባላአምባሻዉ” ሌላዉን ደግሞ ባንድራዬ እያለ የሚጠራዉ ይህንኑ አረንጓዴ፤ ብጫና ቀይ ባንዲራዉን ነዉ። በአንዲት አገራችን ኢትዮጵያ ዉስጥ እነሱም እኛም ለየቅላችን  የኛ የምንለዉ ባንዲራ ሊኖር በፍጹም አይችልም። ይልቅ ወያኔዎች ሲጠፉ እነሱ ይዘዉብን የመጡት ኮተቶ ሁሉ አብሯቸዉ መጥፋቱ አይቀርምና ዛሬ “ባንዲራችን ተደፈረ” ብላችሁ የምታቅራሩ እዉሮች ነገ ከወያኔ በጸዳችዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ጭራሽ ባንዲራ ላይኖራችሁ ይችላልና መጀመሪያ ከራሳችሁ ጋር ቀጥሎም ከአገራችሁ ከኢትዮጵያ ጋር እንድትታረቁ አጥብቄ እማጸናችኋለሁ።

የወያኔን ቂልነትና ባዶነት በሰብኩ ቁጥር ትዝ የምትለኝ አንዲት ቀልድ ብጤ አለችና እስኪ ለፈገግታ ትሆናለችና አዳምጡኝ። ሁለት አመት የፈጀዉ የኤርትራና የኢትዮጵያ አላስፈላጊ ጦርነት እንዳለቀ በጦርነቱ ወቅት ስንቅና ትጥቅ በማመላለስ ትልቅ ዉለታ የዋለች ኣንዲት አህያ ጦርነቱ አብቅቶ የድል በዐል ሲከበር መስቀል አደባባይ ተጋብዛ መለስ ዜናዊ ፊት ትቀርባለች፤ በቋንቋ ይግባቡ ነበርና መለስ ጎንበስ ብሎ በጆሮዋ አንድ ነገር ሹክ ሲላት አህይት በደስታ እየፈነጠዘች አደባባዩን መዞር ጀመረች። በልማታዊ አህይት ዝላይና ፍንጠዛ ግራ የተጋቡት የወያኔ ጋዜጠኞች ዜና ያገኙ መስሏቸዉ “ታላቁ መሪ” ምን አለሽ ብለዉ አህይትን ጠየቋት። የዕድሜ ልክ የህወሓት አባል ሆነሻል ተብያለሁ ብላ አህይት ዝላይዋንና ፍንጠዛዋን ቀጠለች።

ትናንት እዚህ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ የወያኔን ጭፍጨፋ፤ እስርና በዘር መድሎ የተጨማለቀ ስርዐት አበጀህ ቀጥልበት ብለዉ አደባባይ የወጡ ጥቂት ህሊና ቢሶችና እነሱን አመስግኖ የነጻነት አርበኞችን “ዱሪዬዎች” ብሎ የዘለፈዉ የአድር ባዮች ሁሉ አድርባይ የሆነዉ  ግርማ ብሩ ከዚያች ባድመ ላይ ብዙ ስንቅና ትጥቅ ካመላለሰችዉ ጎበዝ አህያ የሚለዩበት መንገድ ቢኖር አህያዋ ማሰብ ስለማትችል አለማሰቧ እነሱ ግን ማሰብ እየቻሉ አለማሰባቸዉ ብቻ ነዉ። በተረፈ እነሱም አህያዋም የወያኔ አባልነታቸዉ ያስደስታቸዋል፤ ምክንያቱም ሁለቱም አያስቡም። መቼም የገዛ ወንድሙና እህቱ ሲታሰሩ፤ ሲደበደቡና  ሲገደሉ አሜን ብሎ ተቀብሎ ነብሰ ገዳዮችን ደግፎ ሰላማዊ ሠልፍ የሚሰለፍ የሰዉ ዘር ያለዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ብቻ መሆን አለበት። ለዚያዉም በወያኔ ዘመን ብቻ!

እነዚህን ሆዳሞች ደግሜ ደጋግሜ እዉሮች እያልኩ የምጠራቸዉ አለምክንያት አይደለም። በእርግጥም ስለማያዩ ነዉ። ባለፈዉ ወር አዚህ አሜሪካ ሚዙሪ ግዛት ፈርግሰን የሚባል ከተማ ዉስጥ ከባድ መሳሪያ የታጠቁ ፖሊሶች መሳሪያቸዉን ሰላማዊ ሰልፈኛዉ ላይ ስላዞሩ (ልብ በሉ ስላዞሩ ነዉ ያልኩት እንጂ ስለተኮሱ አላለኩም እነሱም አላደረጉትም) የአሜሪካ ህዝብ፤ መሪዎችና የህዝብ ተወካዮች ምን ያህል እንደተንጫጩ ሁላችንም ተመልክተናል። እነዚያ እዉሮች ያልኳቸዉ ወንድሞቻችንም  እኛ የተመለከትነዉን ተመልክተዉት ይሆናል፤ ግን እነሱ የአዕምሮ እዉራን ናቸዉና ስዕሉን ብቻ ነዉ እንጂ ቁም ነገሩን አላዩትም። ስለዚህም ነዉ የነሱ ድፕሎማት ተብዬዉ  ድንጋይ ራስ (ርዕስ እምኒ) አዲስ አበባ ዉስጥ ያለ መስሎት ሠላማዊ ሠልፈኛ ለመግደል ደጋግሞ ሲተኩስ አበጀህ ብለዉ ሠላማዊ ሠልፍ የወጡለት።  እግዚአብሄር ከዚህ አይነቱ የአዕምሮ እዉርነት ያድነን! እባካችሁ አሁንም አሜን በሉ። እኔ እያረረ የሚስቅ ማሽላ ብቻ ይመስለኝ ነበር . . . .  ለካስ የገዛ ወገኖቹ ሲገደሉ ደስ ብሎት የሚስቅ ሰዉም አለ። አቤት እግዚኦ!!!!

ሌላዉ የገረመኝ ነገር ቢኖር እነዚህ የአዕምሮ እዉራን ትናንት ረፋዱ ላይ ለአሜሪካዉ ዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጆን ኬሪ በጻፉት ደብዳቤ ግንቦት 7 ያ እንቅልፋም ፓርላማቸዉ “ሽብርተኛ” ብሎ የፈረጀዉ ድርጀት ነዉና ምነዉ ዝም ብላችሁ ታያላችሁ ብለዉ ኬሪን መወትወታቸዉ ነዉ። ኬሪ እንደነሱ ጨካኝና አምባገነን መሪዎች የማይወደዉንና የሚጠላዉን ሁሉ አይንህ አላማረኝም እያለ ማሰር የሚችል መስሏቸዋል። እነዚህ ሆዳቸዉ ልባቸዉን የሸፈነ ከሃዲዎች አይገባቸዉም አንጂ የነሱን “ግንቦት ሰባቶችን” እሰሩልን ብሎ ጥያቄ እንኳን ኬሪ የአለማችን ሀይለኛዉ መሪ አባማም ማስተናገድ አይችልም።  እኛስ ብንሆን የምንታገላቸዉ ለዚሁ ነዉኮ – ኢትዮጵያን የሚመራ ሁሉ ሀሳባችን ከሀሳቡ በተጋጨ ቁጥር አንዳያስረንና እንዳይደገድለን። እኔኮ ምን ይሻለኛል . . . . በአንድ በኩል ኢትዮጵያዉያን የወገኖቻቸዉን መገደል ተቃዉመዉ ሠላማዊ ሠልፍ ሲወጡ የወያኔዉ ተላላኪ ግርማ ብሩ የኤርትራን መንግስት ይከስሳል፤ የአይጥ ምስክር ድንቢጥ እንዲሉ የግርማ ብሩ ተላላኪዎች ደግሞ (የተላላኪ ተላላኪ ማለት ነዉ) ግንቦት ሰባት የሚረዳዉ በኤርትራ መንግስት ነዉና ስጋታችንን እዩልን እያሉ ኬሪን ይለማመጡታል። መቼም አዉቆ የተኛን ቢቀሰቅሱት አይነቃም ነዉና የወያኔ ደጋፊዎች አይገባቸዉም አንጂ ለሻዕቢያ ጎንበስ ቀና እያሉና የሻዕቢያን መሪዎች እንደ ታቦት እየተሳለሙ ለዚህ ዛሬ ላሉበት ደረጃ የበቁት የወያኔ መሪዎች ናቸዉኮ። ዛሬ በባነኑ ቁጥር አንዴ ግንቦት ሰባት አንዴ ሻዕቢያ እያሉ ዛር እንደያዘዉ ሰዉ የሚያጓሩትም ተደምስሰዉ ከታሪክ ምዕራፍ የሚፋቁት በዚሁ እንደ ህጻን ልጅ እጃቸዉን ይዞ ለታሪክ ባበቃቸዉ በሻዕቢያ በኩል መሆኑን በሚገባ ስለሚያዉቁት ብቻ ነዉ። ምድረ የወያኔ አጎብጋቢዎች  ዛሬ እቅጩን ልንገራችሁ፤ ወደዳችሁም ጠላችሁ ይህ “ልማታዊ” ብላችሁ የምትጠሩት ነብሰ ገዳይ አገዛዝ ይደመሰሳል- ስጋታችሁ ትክክለኛ ስጋት ነዉ። ግን ከዚህ ስጋት የሚያድናችሁ ኬሪ ሳይሆን የራሳችሁ ሂሊና ብቻ ነዉና ሳይዉል ሳያድር ዛሬዉኑ ኑና ከህዝብ ጎን ተሰለፉ፤ አለዚያ ዕድላችሁ ከኑግ የተገኘህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ ይሆናል። መቼም እንደኔዉ የዚያች ምስኪን አገር ልጆች ናችሁና በተረት ብነግራችሁ ይገባችኋል ብዬ ነዉ እንጂ በእናንተና መወቀጥ በሚገባዉ ኑግ መካከል ምንም ልዩነት የለም።

የዘረኞቹ የወያኔ መሪዎችና እንደ ችግኝ ኮትኩተዉ ያሳደጓቸዉ ቡችሎቻቸዉ አስቂኝ ታሪክ በዚህ ብቻ አያበቃም፤ እነዚህ ጣምራ ጉደኞች ብዙ ተነግሮ የማያልቅ ጉድ አላቸዉ።  ወያኔዎች ጋዜጠኛ እያሰሩና ከአገር እንዲሰደድ እያደረጉ ተዉ ያላቸዉን ፀረ አገርና ፀረ ልማት ይሉታል፤ በየሰላማዊ ሠልፉ ላይ ንጹህ ዜጎችን በጅምላ ሲጨፈጭፉ ምነዉ ያላቸዉን ደግሞ ሽብርተኛ ብለዉ ያስሩታል። እነዚህ አረመኔዎች  ይህንን የመሰለ ለጆሮ የሚቀፍ ወንጀል በህዝብና በአገር ላይ ፈጽመዉ ሰዎች በነጻነት ወደሚኖሩበት አገር ሰዉ መስለዉ ሲመጡና ስንቃወማቸዉ ደግሞ እዚህ ዉጭ አገር ያስቀመጧቸዉ ተናካሽ ዉሾቻቸዉ “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የጎደላቸዉ ብለዉ ይዘልፉናል። ለመሆኑ ለእነዚህ እንደ ዉሻ ቁራሽ ስጋ በተወረወረላቸዉ ቁጥር ለሚያላዝኑ ምናምንቴዎች ማነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንደነሱ ነዉርን አሜን ብሎ መቀበል ብሎ የነገራቸዉ? ዜጎችን አንደ እንስሳ አየጎተቱ ገድለዉ አስከሬኑን በሟቹ ወንድም እያስጎቱና ይህንን ነዉር በቪድዮ እየቀረጹ መሳቅና መሳለቅ ነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ወይስ  ይህንን ኔሮና ሂትለር ምን አደረጉ የሚያሰኝ ጭካኔና አረመኔነት መቃወም ነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት? አዲስ አበባ ዉስጥና እዚህ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ተቃዋሚ ኃይሎችን “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የጎደላቸዉ ብለዉ የዘለፉት ሬድዋን ሁሴንና ግርማ ብሩ የዉኃ ጠብታን ያክል ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በደማቸዉ ዉስጥ ቢኖር ኖሮ “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የኢትዮጵያዉያንን ህይወት በየአደባባዩ መቀማት አይደለምና እናከብራቸዉ ነበር እንጂ በወጡና በገቡ ቁጥር ስማቸዉን እየጠራን ሌባና ከሃዲ እያልን አናሸማቅቃቸዉም ነበር። ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ስንታሰርና ስንዋረድ እልል፤ ስንገደል ደግሞ አሜን ብለን እንደ በሬ አንገታችንን ለቢለዋ መስጠት ማለት አይደለም። ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ለወገን ማዘን ነዉ፤ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ወገን ሲጎዳና ሲጠቃ ከለላ መሆን ነዉ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ዜጎች ሰቆቃ ሲፈጸምባቸዉና ሲገደሉ ቆሞ ከመመልከት ይልቅ ወይም የገዳዮች ጠበቃ ከመሆን ባጭር ታጥቆ  ነብሰ ገዳዮችንና የጭካኔ ምልክቶችን ከአገር አናትና ከህዝብ ጀርባ ላይ ማስወገድ ነዉ – ወላድ በድባብ ትሂድ – ይህንን የሚያደርጉ የቁርጥ ቀን ልጆች እናት ኢትዮጵያ ትናንንት ነበሯት፤ ዛሬ አሏት ነገም ይኖሯታል።


ወያኔ ሲያስር አሜን….ሲገድልም አሜን

$
0
0

police ethiopia
ከነእምያ

ብዕር የያዘ ማንም ሰዉ በዘመናችን ደግሞ የኮምፒተር መክተቢያ ፊቱ ላይ የደቀነ ሁሉ ከሱ ዉጭ ያለዉን ማንንም ሰዉ “ሌባ”፤ “ባንዳ” ወይም “ከሃዲ” እያለ እንዳሰኘዉ መጻፍ ይችላል። በተለይ በእንደኛ አይነቱ ሀላፊነትም ተጠያቂነትም በሌለበት ህብረተሰብ ዉስጥ ደግሞ የጓደኛዉ ሀሳብ ያልተስማማዉ ሁሉ እየተነሳ የገዛ ጓደኛዉን ባንዳና ከሃዲ አድርጎ ስለሚስለዉ የላይ የላዩን ብቻ ለሚመለከት ሰዉ አገራችን በባንዳና በአገር ወዳድ መሳ ለመሳ ለሁለት የተከፈለች ትመስላለች። እግዝአብሄር ይመሰገን እዉነቱ ግን ከዚህ እጅግ በጣም የተለየ ነዉ። ርዕሴን የጀመርኩት አሜን ብዬ ነዉና እስኪ አንባቢዉ አንተም አሜን በል። ባንዳነትና ከሃዲነት ኃብታምና በእድገት ወደፊት የገፉ አገሮችን እየዘለለ ደሃና ኋላ ቀር አገሮችን ብቻ የሚጠናወት ተራ በሽታ አይደለም። ብዙዎቻችን አምባገነን መሪዎቻችንን ሸሽተን የተጠለልንባት አገር አሜሪካ እነ ሄንሪ ቤስትንና ጆን ብራዉንን የመሳሰሉ ከሃዲዎችን እንዳበቀለች ሁሉ ኢትዮጵያችንም ትናንት እነ ኃ/ሥላሤ ጉግሳን ዛሬ ደግሞ የኃ/ሥላሤ ጉግሳ የልጅ ልጆች የሆኑትን እነ መለስ ዜናዊን፤ አባይ ፀሐዬንና ሰብሃት ነጋን የመሳሰሉ የለየላቸዉ ከሀዲዎችን አፍርታለች። በነገራችን ላይ ሙስሊሙ በዱአዉ፤ ክርስቲያኑ በፀሎት፤ ጠቢብ በጥበቡ ፤ፀሐፊ በምናቡ የባንዳዉንና የከሃዲዉን ብዛት ለመቀነስ ካልተባበሩ በቀር “ወላድ በድባብ ትሂድ” ብለን ባንመርቃቸዉም የባንዳ አባትና አናት አስካሉ ድረስ ባንዳም መወለዱ አይቀርም።
ደጅአዝማች ኃ/ሥላሤ ጉግሳ ማንም ሳያስገድደዉ ወድዶና ፈቅዶ ለወራሪዉ የጣሊያን ጦር ካደረ በኋላ ከጄኔራል ደቦኖ ጋር ሆኖ እናት አገሩን ኢትዮጵያን ወግቷል። ጣሊያኖች ኃ/ሥላሤ ጉግሳ ከነተከታዮቹ ከጎናቸዉ ተሰልፎ አገሩን ሲወጋ ያደረጉት የመጀመሪያዉ ነገር ይህ ከሃዲ ሰዉ ከጎናቸዉ መሰለፉን የሚያሳዩ ፎቶግራፎች ለዓለም ህዝብ ማሰራጨት ነበር። ታሪክ እራሱን ይደግማል ሲባል አይኑ አላይ እያለዉ በጆሮዉ ብቻ ለሰማ ሰዉ ዛሬ ማረጋገጫዉ እነሆ በግልጽ ቀርቦለታል። ትናንት ማክሰኞ መሰከረም 27 ቀን የወያኔ ቴሌቭዥንና ሬድዮ ኢትዮጵያ ዉስጥ በጋዜጠኞች ላይ የሚፈፀመዉን እስርና ስደት፤ ወያኔ በወገኖቻቸን ላይ የሚፈጽመዉን የዕለት ከዕለት ሰቆቃና እንዲሁም በቅርቡ አምቦና ኦጋዴን ዉስጥ የተካሄዱትን የጅምላ ግድያዎች የሚደግፉ የዚህ ዘመን ኃ/ሥላሤ ጉግሳዎች ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ያካሄዱትን የክህደት ሰለማዊ ሠልፍ በተደጋጋሚ ለህዝብ አቅርበዋል። እነዚህ ትናንት ክቡር ባንዲራችን በአለባሌ ሰዉ አንደበት “ጨርቅ” ተብላ ስትሰደብ ከተሳዳቢዉ ሰዉ ጎን ቆመዉ የሳቁና የተሳለቁ ከሃዲ ሆድ አምላኪዎች ዛሬ “ባንዲራችን ተደፈረ” ብለዉ የአዞ እምባ ያነቡብናል። የትኛዉ ባንዲራ? ለመሆኑ እነዚህ “እናቴን ያገባ ሁሉ አባቴ ነዉ” ባዮች ጀግናዉ ዘርዐይ ደረስ ጣሊያኖችን በራሳቸዉ አደባባዮች አንገታቸዉን በጎራዴ የቀላዉ ለዬትኛዉ ባንዲራ እንደሆነ ያዉቃሉ? እነ አብዲሳ አጋ፤ በላይ ዘለቀ፤ ባልቻ አባ ነብሶና እልፍ አዕላፋት የኢትዮጵያ ልጆች ምትክ የሌላትን ህይወታቸዉን የሰጡት ለዬትኛዉ ባንዲራ አንደሆነ ያዉቃሉ?

እነዚህ ወያኔ አዲስ አበባ ዉስጥ የገዛ ወገኖቻዉን ሲያስርና ሲገድል አሜን ብለዉ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ሠላማዊ ሠልፍ የሚወጡ የለየላቸዉ ከሃዲዎች ባንዲራ አዲስ መንግስት በመጣ ቁጥር እንደ ፖሊሲና እንደ ካቢኔ ሚኒስቴር የማይቀያየር ቋሚ የአገር ማንነትና የትዉልድ ትስስር መታወቂያ መሆኑን ሊገነዙ ይገባል። ባንዲራ ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ሊቀየር ይችላል ብለን ብናስብ እንኳን ምን አይነት ሰዎች ብንሆን ነዉ ባንዲራን የመሰለ ህዝብና አገር ማስተሳሰሪያ ማተብ ኢትዮጵያንና ታሪኳን ከልቡ ለሚጠላዉ መለስ ዜናዊና የትግራይ ሪፓብሊክ ካላቋቋምኩ ብሎ ይታገል ለነበረዉ ለከሃዲዉ ስብሀት ነጋ የምንተዉላቸዉ? ደግሞም እነዚህ ምናምንቴዎች አንደሚሉት ባንዲራችን ላይ ባዕድ አካል ሆኖ የተለጠፈዉና የኢትዮጵያ ህዝብ በተለምዶ “ባላ አምባሻዉ” እያለ የሚጠራዉ የወያኔ ጨርቅ እዉነትም ኢትዮጵያ ዉስጥ የብሄር ብሄረሰቦችን እኩልነት አረጋግጦ ቢሆን ኖሮ ዛሬ አገራችን በየቀኑ ብሄር ብሄረሰቦች ዉጣልኝ አልወጣም እየተባባሉ የሚተላለቁባት አገር አትሆንም ነበር። አባቶቻችን የሞቱት ለአረንጓዴ፤ ብጫና ቀይ ባንዲራ ነዉ፤ እኛም ዛሬ በየተሰደድንበት አገር አገሬን እያሰኘ የሚያስጮኸን ይሄዉ አረንጓዴ፤ ብጫ ቀይ ባንዲራችን ነዉ። አገር ቤት ያለዉ ኢትዮጵያዊም አንዱን “ባላአምባሻዉ” ሌላዉን ደግሞ ባንድራዬ እያለ የሚጠራዉ ይህንኑ አረንጓዴ፤ ብጫና ቀይ ባንዲራዉን ነዉ። በአንዲት አገራችን ኢትዮጵያ ዉስጥ እነሱም እኛም ለየቅላችን የኛ የምንለዉ ባንዲራ ሊኖር በፍጹም አይችልም። ይልቅ ወያኔዎች ሲጠፉ እነሱ ይዘዉብን የመጡት ኮተቶ ሁሉ አብሯቸዉ መጥፋቱ አይቀርምና ዛሬ “ባንዲራችን ተደፈረ” ብላችሁ የምታቅራሩ እዉሮች ነገ ከወያኔ በጸዳችዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ጭራሽ ባንዲራ ላይኖራችሁ ይችላልና መጀመሪያ ከራሳችሁ ጋር ቀጥሎም ከአገራችሁ ከኢትዮጵያ ጋር እንድትታረቁ አጥብቄ እማጸናችኋለሁ።

የወያኔን ቂልነትና ባዶነት በሰብኩ ቁጥር ትዝ የምትለኝ አንዲት ቀልድ ብጤ አለችና እስኪ ለፈገግታ ትሆናለችና አዳምጡኝ። ሁለት አመት የፈጀዉ የኤርትራና የኢትዮጵያ አላስፈላጊ ጦርነት እንዳለቀ በጦርነቱ ወቅት ስንቅና ትጥቅ በማመላለስ ትልቅ ዉለታ የዋለች ኣንዲት አህያ ጦርነቱ አብቅቶ የድል በዐል ሲከበር መስቀል አደባባይ ተጋብዛ መለስ ዜናዊ ፊት ትቀርባለች፤ በቋንቋ ይግባቡ ነበርና መለስ ጎንበስ ብሎ በጆሮዋ አንድ ነገር ሹክ ሲላት አህይት በደስታ እየፈነጠዘች አደባባዩን መዞር ጀመረች። በልማታዊ አህይት ዝላይና ፍንጠዛ ግራ የተጋቡት የወያኔ ጋዜጠኞች ዜና ያገኙ መስሏቸዉ “ታላቁ መሪ” ምን አለሽ ብለዉ አህይትን ጠየቋት። የዕድሜ ልክ የህወሓት አባል ሆነሻል ተብያለሁ ብላ አህይት ዝላይዋንና ፍንጠዛዋን ቀጠለች።

washington dc 3
ትናንት እዚህ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ የወያኔን ጭፍጨፋ፤ እስርና በዘር መድሎ የተጨማለቀ ስርዐት አበጀህ ቀጥልበት ብለዉ አደባባይ የወጡ ጥቂት ህሊና ቢሶችና እነሱን አመስግኖ የነጻነት አርበኞችን “ዱሪዬዎች” ብሎ የዘለፈዉ የአድር ባዮች ሁሉ አድርባይ የሆነዉ ግርማ ብሩ ከዚያች ባድመ ላይ ብዙ ስንቅና ትጥቅ ካመላለሰችዉ ጎበዝ አህያ የሚለዩበት መንገድ ቢኖር አህያዋ ማሰብ ስለማትችል አለማሰቧ እነሱ ግን ማሰብ እየቻሉ አለማሰባቸዉ ብቻ ነዉ። በተረፈ እነሱም አህያዋም የወያኔ አባልነታቸዉ ያስደስታቸዋል፤ ምክንያቱም ሁለቱም አያስቡም። መቼም የገዛ ወንድሙና እህቱ ሲታሰሩ፤ ሲደበደቡና ሲገደሉ አሜን ብሎ ተቀብሎ ነብሰ ገዳዮችን ደግፎ ሰላማዊ ሠልፍ የሚሰለፍ የሰዉ ዘር ያለዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ብቻ መሆን አለበት። ለዚያዉም በወያኔ ዘመን ብቻ!

እነዚህን ሆዳሞች ደግሜ ደጋግሜ እዉሮች እያልኩ የምጠራቸዉ አለምክንያት አይደለም። በእርግጥም ስለማያዩ ነዉ። ባለፈዉ ወር አዚህ አሜሪካ ሚዙሪ ግዛት ፈርግሰን የሚባል ከተማ ዉስጥ ከባድ መሳሪያ የታጠቁ ፖሊሶች መሳሪያቸዉን ሰላማዊ ሰልፈኛዉ ላይ ስላዞሩ (ልብ በሉ ስላዞሩ ነዉ ያልኩት እንጂ ስለተኮሱ አላለኩም እነሱም አላደረጉትም) የአሜሪካ ህዝብ፤ መሪዎችና የህዝብ ተወካዮች ምን ያህል እንደተንጫጩ ሁላችንም ተመልክተናል። እነዚያ እዉሮች ያልኳቸዉ ወንድሞቻችንም እኛ የተመለከትነዉን ተመልክተዉት ይሆናል፤ ግን እነሱ የአዕምሮ እዉራን ናቸዉና ስዕሉን ብቻ ነዉ እንጂ ቁም ነገሩን አላዩትም። ስለዚህም ነዉ የነሱ ድፕሎማት ተብዬዉ ድንጋይ ራስ (ርዕስ እምኒ) አዲስ አበባ ዉስጥ ያለ መስሎት ሠላማዊ ሠልፈኛ ለመግደል ደጋግሞ ሲተኩስ አበጀህ ብለዉ ሠላማዊ ሠልፍ የወጡለት። እግዚአብሄር ከዚህ አይነቱ የአዕምሮ እዉርነት ያድነን! እባካችሁ አሁንም አሜን በሉ። እኔ እያረረ የሚስቅ ማሽላ ብቻ ይመስለኝ ነበር . . . . ለካስ የገዛ ወገኖቹ ሲገደሉ ደስ ብሎት የሚስቅ ሰዉም አለ። አቤት እግዚኦ!!!!

ሌላዉ የገረመኝ ነገር ቢኖር እነዚህ የአዕምሮ እዉራን ትናንት ረፋዱ ላይ ለአሜሪካዉ ዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጆን ኬሪ በጻፉት ደብዳቤ ግንቦት 7 ያ እንቅልፋም ፓርላማቸዉ “ሽብርተኛ” ብሎ የፈረጀዉ ድርጀት ነዉና ምነዉ ዝም ብላችሁ ታያላችሁ ብለዉ ኬሪን መወትወታቸዉ ነዉ። ኬሪ እንደነሱ ጨካኝና አምባገነን መሪዎች የማይወደዉንና የሚጠላዉን ሁሉ አይንህ አላማረኝም እያለ ማሰር የሚችል መስሏቸዋል። እነዚህ ሆዳቸዉ ልባቸዉን የሸፈነ ከሃዲዎች አይገባቸዉም አንጂ የነሱን “ግንቦት ሰባቶችን” እሰሩልን ብሎ ጥያቄ እንኳን ኬሪ የአለማችን ሀይለኛዉ መሪ አባማም ማስተናገድ አይችልም። እኛስ ብንሆን የምንታገላቸዉ ለዚሁ ነዉኮ – ኢትዮጵያን የሚመራ ሁሉ ሀሳባችን ከሀሳቡ በተጋጨ ቁጥር አንዳያስረንና እንዳይደገድለን። እኔኮ ምን ይሻለኛል . . . . በአንድ በኩል ኢትዮጵያዉያን የወገኖቻቸዉን መገደል ተቃዉመዉ ሠላማዊ ሠልፍ ሲወጡ የወያኔዉ ተላላኪ ግርማ ብሩ የኤርትራን መንግስት ይከስሳል፤ የአይጥ ምስክር ድንቢጥ እንዲሉ የግርማ ብሩ ተላላኪዎች ደግሞ (የተላላኪ ተላላኪ ማለት ነዉ) ግንቦት ሰባት የሚረዳዉ በኤርትራ መንግስት ነዉና ስጋታችንን እዩልን እያሉ ኬሪን ይለማመጡታል። መቼም አዉቆ የተኛን ቢቀሰቅሱት አይነቃም ነዉና የወያኔ ደጋፊዎች አይገባቸዉም አንጂ ለሻዕቢያ ጎንበስ ቀና እያሉና የሻዕቢያን መሪዎች እንደ ታቦት እየተሳለሙ ለዚህ ዛሬ ላሉበት ደረጃ የበቁት የወያኔ መሪዎች ናቸዉኮ። ዛሬ በባነኑ ቁጥር አንዴ ግንቦት ሰባት አንዴ ሻዕቢያ እያሉ ዛር እንደያዘዉ ሰዉ የሚያጓሩትም ተደምስሰዉ ከታሪክ ምዕራፍ የሚፋቁት በዚሁ እንደ ህጻን ልጅ እጃቸዉን ይዞ ለታሪክ ባበቃቸዉ በሻዕቢያ በኩል መሆኑን በሚገባ ስለሚያዉቁት ብቻ ነዉ። ምድረ የወያኔ አጎብጋቢዎች ዛሬ እቅጩን ልንገራችሁ፤ ወደዳችሁም ጠላችሁ ይህ “ልማታዊ” ብላችሁ የምትጠሩት ነብሰ ገዳይ አገዛዝ ይደመሰሳል- ስጋታችሁ ትክክለኛ ስጋት ነዉ። ግን ከዚህ ስጋት የሚያድናችሁ ኬሪ ሳይሆን የራሳችሁ ሂሊና ብቻ ነዉና ሳይዉል ሳያድር ዛሬዉኑ ኑና ከህዝብ ጎን ተሰለፉ፤ አለዚያ ዕድላችሁ ከኑግ የተገኘህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ ይሆናል። መቼም እንደኔዉ የዚያች ምስኪን አገር ልጆች ናችሁና በተረት ብነግራችሁ ይገባችኋል ብዬ ነዉ እንጂ በእናንተና መወቀጥ በሚገባዉ ኑግ መካከል ምንም ልዩነት የለም።

የዘረኞቹ የወያኔ መሪዎችና እንደ ችግኝ ኮትኩተዉ ያሳደጓቸዉ ቡችሎቻቸዉ አስቂኝ ታሪክ በዚህ ብቻ አያበቃም፤ እነዚህ ጣምራ ጉደኞች ብዙ ተነግሮ የማያልቅ ጉድ አላቸዉ። ወያኔዎች ጋዜጠኛ እያሰሩና ከአገር እንዲሰደድ እያደረጉ ተዉ ያላቸዉን ፀረ አገርና ፀረ ልማት ይሉታል፤ በየሰላማዊ ሠልፉ ላይ ንጹህ ዜጎችን በጅምላ ሲጨፈጭፉ ምነዉ ያላቸዉን ደግሞ ሽብርተኛ ብለዉ ያስሩታል። እነዚህ አረመኔዎች ይህንን የመሰለ ለጆሮ የሚቀፍ ወንጀል በህዝብና በአገር ላይ ፈጽመዉ ሰዎች በነጻነት ወደሚኖሩበት አገር ሰዉ መስለዉ ሲመጡና ስንቃወማቸዉ ደግሞ እዚህ ዉጭ አገር ያስቀመጧቸዉ ተናካሽ ዉሾቻቸዉ “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የጎደላቸዉ ብለዉ ይዘልፉናል። ለመሆኑ ለእነዚህ እንደ ዉሻ ቁራሽ ስጋ በተወረወረላቸዉ ቁጥር ለሚያላዝኑ ምናምንቴዎች ማነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንደነሱ ነዉርን አሜን ብሎ መቀበል ብሎ የነገራቸዉ? ዜጎችን አንደ እንስሳ አየጎተቱ ገድለዉ አስከሬኑን በሟቹ ወንድም እያስጎቱና ይህንን ነዉር በቪድዮ እየቀረጹ መሳቅና መሳለቅ ነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ወይስ ይህንን ኔሮና ሂትለር ምን አደረጉ የሚያሰኝ ጭካኔና አረመኔነት መቃወም ነዉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት? አዲስ አበባ ዉስጥና እዚህ ዋሺንግተን ዲሲ ዉስጥ ተቃዋሚ ኃይሎችን “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የጎደላቸዉ ብለዉ የዘለፉት ሬድዋን ሁሴንና ግርማ ብሩ የዉኃ ጠብታን ያክል ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በደማቸዉ ዉስጥ ቢኖር ኖሮ “ኢትዮጵያዊ ጨዋነት” የኢትዮጵያዉያንን ህይወት በየአደባባዩ መቀማት አይደለምና እናከብራቸዉ ነበር እንጂ በወጡና በገቡ ቁጥር ስማቸዉን እየጠራን ሌባና ከሃዲ እያልን አናሸማቅቃቸዉም ነበር። ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ስንታሰርና ስንዋረድ እልል፤ ስንገደል ደግሞ አሜን ብለን እንደ በሬ አንገታችንን ለቢለዋ መስጠት ማለት አይደለም። ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ለወገን ማዘን ነዉ፤ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ወገን ሲጎዳና ሲጠቃ ከለላ መሆን ነዉ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ዜጎች ሰቆቃ ሲፈጸምባቸዉና ሲገደሉ ቆሞ ከመመልከት ይልቅ ወይም የገዳዮች ጠበቃ ከመሆን ባጭር ታጥቆ ነብሰ ገዳዮችንና የጭካኔ ምልክቶችን ከአገር አናትና ከህዝብ ጀርባ ላይ ማስወገድ ነዉ – ወላድ በድባብ ትሂድ – ይህንን የሚያደርጉ የቁርጥ ቀን ልጆች እናት ኢትዮጵያ ትናንንት ነበሯት፤ ዛሬ አሏት ነገም ይኖሯታል።

ዛሬም ሆነ ነገ ፕሮፌሠር አሥራት ወልደዬስ የተለሙልን ፈለግ የትውልዳችን ቃልኪዳን ይሁን!

$
0
0

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ለምን እና እንዴት ተመሠረተ?

Moreshልክ የዛሬ ፪(ሁለት) ዓመት መስከረም ፳፯ ቀን ፪ሺህ፭ ዓ.ም.፣ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ተመሠረተ። ለድርጅቱ መመሥረት ዋና መሠረታዊ ምክንያቱ ኢትዮጵያዊነቱን በምንም ዓይነት ጥርጥር ውስጥ አስገብቶ የማያውቀው ዐማራ የተጋረጠበት የኅልውና መጥፋት አደጋ እንደሆነ አያጠራጥርም። በተለይም ደግሞ የዐማራው ታሪካዊ ጠላቶች በትግሬ-ወያኔ አገዛዝ አሰባሣቢነት ተቧድነው ባለፉት ፵(አርባ) ዓመታት ያደረጉበት የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሲሆን፣ የጥፋቱ እና የግፉ ብዛትም ሆነ ግዝፈት በዮዲት ጉዲት እና በግራኝ አሕመድ የጥፋት ዘመኖች በዐማራው ላይ ከተፈፀሙት ጭፍጨፋዎች ቢበልጥ እንጂ የማያንስ ነው። ስለሆነም ለሞረሽ-ወገኔ መመሥረት ቆስቋሽ የሆነው ምክንያት፣ ከየካቲት እስከ ሰኔ ፪ሺህ፬ ዓ.ም. በደቡብ ኢትዮጵያ ጉራፈርዳ ወረዳ ይኖሩ በነበሩ ከ፸፰(ሰባ ስምንት) ሺህ የሚልቁ የዐማራ ወገኖቻችን ላይ የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ያካሄደው የዘር ማጽዳት ዘመቻ ነበር።

የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ድርጊት በሁሉም የዓለም ክፍሎች ተበትነው በሚኖሩ የዐማራ ነገድ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ላይ ከፍተኛ የሆነ የመጠቃት ስሜትን መጫሩ እይታበልም። በመሆኑም ናዚያዊው አገዛዝ በሥልጣን ላይ ከተቆናጠጠበት ጊዜ ጀምሮ በዐማራው ነገድ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚያካሂደውን የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ ለማስቆም፣ የዐማራው ልጆች ያላቸው ብቸኛው አማራጭ መንገድ ተደራጅቶ መታገል መሆኑን ከዘገየም በኋላ ለመገንዘብ በቅተዋል። ይህንን ነባራዊ ሁኔታ የተገነዘቡ እና ለችግሩም ተግባራዊ ምላሽ ለመስጠት ቁርጠኛ የሆኑ፣ በዓለም ዙሪያ የሚኖሩ ከሠላሣ የማይበልጡ የዐማራው ልጆች ከያሉበት ተጠራርተው አንድ ለዐማራው መብት መጠበቅ የሚታገል ድርጅት ማቋቋም ስለሚቻልበት መንገድ መምከር ያዙ። በምክር ብቻ አልተገቱም፤ ከ፭(አምሥት) ወራት ያላሠለሰ ጥረት በኋላ በመስከረም ፳፮ እና ፳፯ ቀን ፪ሺህ፭ ዓ.ም. መሥራች ጉባኤ አካሂደው በጉባኤያቸው ማብቂያ ለዐማራው ኅልውና መጠበቅ ቋሚ ጠበቃ የሆነ ድርጅት መመሥረታቸውን ለዓለም ይፋ አደረጉ። ለድርጅቱም መጠሪያ ዐማራው ለችግር ጊዜ «የድረሱልኝ» ጥሪ ማሠሚያ ባደረገው ቃል «ሞረሽ» የሚል ቅፅል እንዲጨመርበት ሙሉ ስምምነት ላይ ደረሱ። እነሆ ዛሬ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ፪(ሁለት) ዓመት ያስቆጠረ በሁለት እግሩ የቆመ ጨቅላ ለመሆን በቅቷል።

በኢትዮጵያ በ፲፱፻፶ዎቹ(1950ዎቹ) ከተጠነሰሰው የተማሪዎች የለውጥ እንቅስቃሴ ጀምሮ አንድ በሕግ መልክ ተረቅቆ ያልወጣ፣ ግን ዐማራው በዐማራነቱ ተደራጅቶ ለነገዱ እና ለአገሩ ለኢትዮጵያም ዘላቂ ኅልውና መጠበቅ እንዳይታገል ታሪካዊ ጠላቶቹ የሸበቡበት የተንኮል አሽክላ ነበር። እርሱም «ዐማራው በኢትዮጵያዊነቱ ብቻ እንጂ በዐማራነቱ አይደራጅም።» የሚል አጉል ሽንገላን ያዘለ ክፉ የማደንዘዣ አዚም። የሞረሽ-ወገኔ የዐማራ ድርጅት መመሥረት በ፲፱፻፹፬ ዓ.ም. በታላቁ የሕክምና ባለሙያ ፕሮፌሠር አሥራት ወልደየስ ኢትዮጵያ ውስጥ የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት (መዐሕድ) ከተቋቋመ ወዲህ በውጭ አገሮች የሚኖሩ ዐማራ ኢትዮጵያውያን ለነገዳቸው እና ለአገራቸው ኅልውና መጠበቅ ሲሉ ያከናወኑት ትልቅ የዕመርታ እርምጃ ሆኖ ሊወሰድ ይችላል።

ድርጅቱ ኅልውናውን ከተቀዳጀ በኋላ ምን፣ ምን ተግባሮችን አከናወነ?

ሞረሽ-ወገኔ ተመሥርቶ በይፋ እንቅስቃሴውን ማካሄድ ከጀመረበት ከመስከረም ፳፯ ቀን ፪ሺህ፭ ዓ.ም. ጀምሮ ቀዳሚ ተግባሩ አድርጎ የወሰደው፣ በሁሉም የዓለም ክፍሎች ተበትነው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዐማሮችን ማንቃት እና በድርጅቱ ጥላ ሥር ማደራጀትን ነው። ድርጅቱ በዓለም ዙሪያ ያሉ ዐማሮችን ለመቀስቀስ ከ፷(ስድሳ) የማያንሱ ወቅታዊ መግለጫዎችን፣ በጥናት ላይ የተመሠረቱ ታሪካዊ ዳራ ያላቸው ጽሑፎችን፣ እንዲሁም በድምፅ እና በምሥል የታጀቡ ቅንብሮችን፣ የዘመኑን የኢትተርኔት ቴክኖሎጂን ጨምሮ በተገኙት አጋጣሚዎች ሁሉ በመጠቀም አሠራጭቷል። እንዲሁም በሁሉም የዓለማችን ክፍሎች ስለድርጅቱ እንቅስቃሴ የሚያስተዋውቁ ከ፳(ሃያ) የማያንሱ ሕዝባዊ ስብሰባዎችን አካሂዷል። በእንቅስቃሴውም ገና ከጅምሩ መልካም ፍሬን አፍርቶ፣ በሁሉም የዓለማችን አኅጉሮች የሚኖሩ ዐማራ ኢትዮጵያውያንን ለማሰባሰብ እና የድርጅቱን አካሎች ለማቋቋም ተችሏል። በአውሮፓ እና በአውስትራሊያ ከመሠረታዊ እስከ አኅጉር-አቀፍ ቅርንጫፎች ተዋቅረዋል። በካናዳ እና በተባበሩት የአሜሪካ ግዛቶችም ከመሠረታዊ ማኅበር እስከ አገር-አቀፍ ቅርንጫፎች ድረስ ደረጃ ደረጃ የማዋቀር ተግባሩ ቀጥሏል። መደራጀት በራሱ ብቻውን የትግሉ ግብ ባይሆንም ለዐማራው ነገድ ኅልውና፣ ብሎም ለኢትዮጵያ ዘለቄታዊነት መቀጠል ይህ የመጀመሪያው ወሣኝ ተግባር መሆኑ ግን አያወላውልም።

በዚህ አጭር ዕድሜው ሞረሽ-ወገኔ ካከናወናቸው ታላላቅ ብሔራዊ ግዳጅን የሚመለከቱ ተግባሮች አንዱ የታላቁን የኢትዮጵያ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ አፄ ምኒልክን ታሪካዊ አስተዋፅዖ በአዲሱ ትውልድ እንዲዘከር ማድረጉ ነው። እንደሚታወቀው ዳግማዊ አፄ ምኒልክ የዘመናዊት ኢትዮጵያ መሥራች አባት፣ የጥቁር ሕዝብ መኩሪያ የሆነው የታሪካዊው የአድዋ ጦርነት ድል አድራጊ መሪ፣ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸውም ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር እንዲተዋወቁ መሠረታዊ በሆነ የለውጥ ሂደት እንዲያልፉ ያደረጉ ብልህ እና ጀግና መሪያችን ነበሩ። ሆኖም «የእሣት ልጅ አመድ» ሆኖ ተከታዩ ትውልድ እንኳን የእርሣቸውን የአገር ግንባታ ትልም ሊከተል ቀርቶ ባንዶች እና የባንዳ ልጆች የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ሕይወት እስከመምራት ደርሰዋል። እኒያ የአድዋን ድል ያስገኙ ጀግኖች አያቶቻችን እና ቅድመ-አያቶቻችን ዛሬ በሕይዎት ኖረው ቢሆን ኖሮ ምን ይሉ ይሆን? ስለዚህም ከታሪክ እና ከትውልድ ተወቃሽነት ለመዳን፣ ሞረሽ-ወገኔ የኢትዮጵያን የረዥም ዘመን ታሪክ ሣያዛባ በኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዲዘከር ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል።

ሞረሽ-ወገኔ ለወደፊት ምን ዓይነት ተልዕኮዎችን ለመወጣት ተሠናድቷል?

ከከ፵(አርባ) ዓመታት በፊት በመላ ኢትዮጵያ በዐማራው ላይ የታወጀው የዕልቂት ዘመቻ፣ ከዘመን ዘመን እየተሸጋገረ ዛሬ ያለንበት እጅግ አስከፊው ደረጃ ላይ ደርሷል። በተለይም የትግሬ-ወያኔ ናዚያዊ ቡድን በ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. በወልቃይት-ጠገዴ በሚኖሩ ዐማራ ኢትዮጵያውያን የጀመረውን የዘር ማጥፋት እና የዘር ማፅዳት ዘመቻ አስፋፍቶ በአሁኑ ወቅት በሁሉም የአገሪቱ ማዕዘኖች በሚኖሩ ዐማሮች ላይ አዳርሶታል። ሰሞኑንም በጋምቤላ ክልል፣ መዠንግር ዞን፣ በሜጢ ከተማ እና በአካባቢው በዐማራ ነገድ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈፀመው ድርጊት የዚያው የመጀመሪያው የትግሬ-ወያኔ ፖሊሲ ውጤት መሆኑ አያጠያይቅም። ስለዚህ ዐማራው ዘለቄታዊ ኅልውናውን ለማስጠበቅ ምን ማድረግ አለበት?

በመጀመሪያ የችግሩን መኖር መቀበል ይገባል፥ ኢትዮጵያውያን ዐማሮች የዘር ማፅዳት እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶብን እያለቅን ነው።

ተከታታዩ እርምጃ፥ መደራጀት፣ መደራጀት፣ መደራጀት። በምን መልክ? ዐማራው ኢትዮጵያዊነቱን ሣይለቅ በዐማራነቱ መደራጀት አለበት። ሞረሽ-ወገኔም ዘወትር ጥሪውን የሚያቀርበው ዐማራው በዙሪያው እንዲደራጅ ነው።

ትግል ካሉበት አካባቢ ይጀምራል። በተለይ በስደት የሚኖረው ዐማራ በሚኖርበት አካባቢ የሚገኙ አብያተ-ክርስቲያን፣ መስጊዶችን፣ የኢትዮጵያውያን የሆኑ የተለያዩ የማኅበረሰብ ተቋሞችን እና ድርጅቶች በግዴለሽነት ወይም በቸልተኝነት ለትግሬ-ወያኔዎች እና ለሌሎች ፀረ-ኢትዮጵያ ኃይሎች እያስረከበ፤ በተቃራኒው ግን የኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን መሠረታዊ ጠላት በሆነው «በሻቢያ ጥላ ከለላነት ወያኔን በትጥቅ ትግል ተፋልመን ኢትዮጵያን ነፃ እናወጣለን» ከሚለው የጅሎች የቀን ቅዠት ሊነቃ ይገባዋል። ስለሆነም በመጀመሪያ የዕምነት ተቋሞቹን ማስከበር፤ የማኅበረሰብ መሰባሰቢያ መድረኮችን ከሻቢያ፣ ከትግሬ-ወያኔ እና ከመሠል ፀረ-ኢትዮጵያ ኃይሎች መንጋጋ የማላቀቅ ኃላፊነቱ የእርሱው መሆኑን ተገንዝቦ ለተግባራዊ ምላሽ መንቀሳቀስ ይገባዋል። ከዚያ ወደሚቀጥለው የተግባር ምዕራፍ መሸጋገር ይቻላል።

በአገሩ በኢትዮጵያ የዜግነት መብቱን ነፍገው፣ ፍትኅ አሳጥተው፣ ለአስከፊው እና መራሩ የስደት ሕይዎት የዳረጉት የትግሬ-ወያኔ ቀንደኛ ባለሥልጣኖች፣ በውጪ አገሮች እንደርሱው ስደተኛ መስለው መጥተው አፉን ሊሸብቡት አይገባም። ባለፉት ፳፫(ሃያ ሦሥት) ዓመታት አያሌ የትግሬ-ወያኔ ቀንደኛ ነፍሰገዳዮች ወደውጪ አገሮች በ«ስደት» ስም ወጥተዋል። ሆኖም በኢትዮጵያውያን ላይ ለፈፀሟቸው ኢሰብአዊ ግፎች አንዳቸውም እንኳን በፍርድ ችሎት ቀርበው አያውቁም። ይህ ሁኔታ ሊያበቃ ይገባዋል።

ለማጠቃለል፥ ዐማራ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፦ አባቶቻችን፣ እናቶቻችን፣ አያቶቻችን፣ ቅድመ-አያቶቻችንም ሆነ የቀደሙት ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ነፃነታቸውን አስከብረው፣ ሙሉ አገር ያስረከቡን ከማንም ባገኙት ችሮታ አይደለም። ስለዚህ በዐማራነታችን ተደራጅተን የነገዳችንን ዘለቄታዊ ኅልውና እናስከብር፤ ይህንንም በማድረግ የውዲቷን አገራችንን የኢትዮጵያን ዳግም ትንሣኤ እናፋጥን።

 

ዐማራን ከፈፅሞ ጥፋት እንታደጋለን!

ፈለገ-አሥራት የትውልዳችን ቃልኪዳን ነው!

ኢትዮጵያ በቆራጥ እና ታማኝ ልጆቿ መስዋዕትነት ለዘለዓለም ታፍራና ተከብራ ትኖራለች!

የጥይት ሩምታ በሰንደቅዓላማችን ላይ …. ጥጋቡ መረን ለቀቀ።

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 10.10.2014 /ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ/


“ያልወለድኩት ቢለኝ ባባ አፌን አለኝ ዳባ – ዳባ”
እኔ አይደለሁም ዘመኑን በተደሞና በአርምሞ እንዲሁም በፅሞና ሲከታተል ባጅቶ – የከረመው፤ እሰኪበቃው ድረስ በወያኔ 40 ዓመት ሙሉ በቋሳና በቁርሾ የተቀጠቀጠው የኢትዮጵያ ሰንድቅአላማ ነው በመንፈሱ  – የተቃኘው። ለመሆኑ ዬት የሚያውቀውን ሰንድቅዓላማ ነው እንዲህ ወያኔ የሚዘባነነው?! በዚህ ሰንደቅዓላማ ተከብራና ታፍራ የኖረች ሀገር አታስፈልገኝም፣ ገዝታኛለች በማለት አይደለም ትግራይን ከኢትዮጵያ ነጥሎ “የታላቋን ትግራይ” ህልም ለማሳካት እርጥብ ጌሾውን በቂም ምቸት ጠንስሶ ሲዳከር የኖረው። ቀድሞ ነገር በወያኔ ሃርነት ትግራይ ማዕቀፍ ውስጥ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት የተፋቀ ነው። ከዚህ መንፈስ ሳትወጡ በጥልቀት መርምሩት …. በሌለ – ባልነበረ –  በአመለ መንፈስ የበቀለ የባዕድ ህልም ተጓዥ በምን ስሌት ነው ዛሬ አጃቢዎቹ ተቆርቋሪነቱን የሚያንኳኩለት ወይንም የሚያንኮሻኩሹለት? …. በዚህ ብሄራዊ ሰንድቅዓላማ ዙሪያ መንፈሱ የወያኔ ሃርነት ትግራይ ኖሮ በፍጹም አያውቅም? መቼ – በዬትኛው ዘመንስ? እስኪ ጫካ እያለ የኢትዮጵያ ሰንድቅአላማ ንጹህ ምስሉን፣ ገጹን በወያኔ ሃርነት ጉባኤዎች ላይ ዬት ላይ ተከብሮ ታደመ? – እንዲሳተፍስ በዬትኛው የወያኔ ሃርነት ጉባኤ ላይ ተፈቀደለት? ምን ያህል ነፃነት ተሰጠው? ይህ እኮ ተፈጥሮው ያልተነነ የዕውነት መሰረተ – ጉልት ነው። ወያኔ በለስ ቀንቶት ከጫካ ወደ ከተማ ሲገባ ለምስል አንድ ቦታ ላይ የኢትዮጵያ ሰንደቅአላማ ያያዘ ሰራዊት ሆነ መሪ አይታችኋልን?! ፈጽሞ አኮ በኢትዮጵያዊነት ሙጣጭ መንፈስ በሌለው ጭድ ግንዛቤ እኮ ነው ሀገር እንዲህ እዬታመሰ ያለው። ወያኔ ከኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ውጪ የነበረ፣ ያለ – ወደፊትም የሚኖር መሆኑን እውነትን የመቀበል አቅማችን ጋር እባካችሁ ወገኖቼ እንነጋገር። የእኔ ያልሆነው የእኔ ሊሆን ከቶ አይችልም። ለዚህ ነው ከወያኔ አስተምኽሮ የመነሳትን አስፈላጊነት በአጽህኖት ሳልታክት የማሳስበው። ውዶቼ – የኔዎቹ ከዚህ ከተነሳችሁ መንገዱ ቀላል ነው ….

ethiopian-human-rights-activits

የእናት ኢትዮጵያ ያ ወ/ሮ ሞንዳላ ሙሉ ቅርፆዋ እኮ ለወያኔ በሽታው ነው የነበረው። በመንፈስና በአካሏ ተበትና አቅመ ቢስ ስትሆንለት የተነሳበትን ቁርሾ አሳካለሁ ብሎ አይደል ዘመን ይቅር የማይለውን ዘር አምካኝ ድርጅት ወያኔ ሃርነት ትግራይን የተከለው። አረሙ ወያኔ በተጠመጠመ ትብትብ ተብትቦ ነገር እያፈላ ዛሬ ያለችበትን የሞትና የህይወት ግብግብ አና ብሎ ፈጠረ። ተሳክቶለት ሁሉን የመያዝ ዕድሉን አግኝቶ እንኳን ለሰከንድ ሳይዘናጋ ዘነዘናዋን አስቀርቶ እዬገዘገዛት ይገኛል። ሰንደቅዓላማው መቼ ተፈጥረ ብሎ እንደዘገበው ተመልከቱት … “የተፈጠረበት ዓመት ሰንድቅዓላማው በግዕዙ የተጻፈው ቀን ሲተረጎም “ጥር 28 ቀን 1988 ዓም.” ምን? “የተፈጠረበት ዓመት” ታሪክን፤ ትውፊትን – የፈሰሰ ደምን፣ የተከሰከሰን አጥንት ሁሉ ዋጋ አልባ አደረገው። በቁሙ ገድሎ የሚቀብር ዝክንትል ህልም። ለዚህ የላሸቀ ብክነት ነው ፋሽኮው ቀለብ የሚሰፈርለት ሲጮህ የምታዳምጡት ….

http://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1

የኔዎቹ ውዶቼ – ማናቸውም አንጡራ የሃብት ዘረፋው ደግሞ የመንፈሱንም ጨምሮ ለዬትኛው ተልዕኮ ማስፈጻሚያ እንደሚውል “ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ ነው።” ጡጦ የሚጠባ ልጅ እኮ አይደለም የኢትዮጵያ ህዝብ። …. እራሱ ብክሉ መንፈስ ከዚህ አጥፊ ድርጅት አፈነገጥኩ የሚለው ጥንስስ ድርጅት ሁሉ ከዚህ አዟሪት የመውጣት አቅም የለውም። …. ሽባ ነው። ይህ ማለት ጥላቻው ሥር ሰደድ መርህ መሆኑን ማመሳክር ይቻላል። እሩቅ ሳይኬድ ይህችን ነጠላ አምክንዮ ይዛችሁ ብትፈትሿት።

እ.ኤ.አ ጥቅምት 5.ቀን 2014 እዚህ ሲዊዘርላንድ ዙሪክ በብራዚል ቆንሲላ ጽ/ቤት ብራዚላውያን በሀገራዊው ምርጫ ሲሳተፉ መዋላቸውን ቴሌ ዙሪ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ሲዘግብ አዳመጥኩኝ። ሰልፉንም አዬሁኝ። ህሊና ያለው፤ ባለቤትነት የሚሰማው፤ የህዝብን ድምጽ የማይፈራ፤ ዬህዝብ ድምጽ አስፈላጊነት የመተርጎም አቅም የተሰጠው፤ እንዲሁም ዘመኑ ለሰው ልጆች የለገሰውን የመብት ነፃነት ያልነፈገ ተግባር እንዲህ ባደላቸው ሀገሮች ይፈጸማል። የሌሎች ሀገር ዜጎች ተሰደውም ሁነኛ አላቸው፤ እረኛ አላቸው፤ ባሊህ ባይ አላቸው – ።

ብራዚላውያን እዚህ ሲውዘርላንድ ላይ ምርጫው ላይ እንዲሳተፉ በክብር ተጠሩ፤ የቻሉት በቦታው ተገኝተው ሲመርጡ ዋሉ። አንዲት ቃለ ምልልስ የተደረገላቸው ወ/ሮ ሲገልጹ እንደሰማሁት ሶስት ሰአት እንደጠበቁ አዳምጫለሁ። ማለት በርካታ ብራዚላውያን ሙሉ ቀን ድምጻቸውን ሲሰጡ እንደዋሉ ተረድቻለሁ። አሁን ወደ እኛ የእንሰሳ አስተዳደር ስንመጣ፤ አይደለም ውጪ የሚገኘው ወገን በሀገሩ ጉዳይ እኩል መሳተፍ እንዲችል መብቱን በሚያረጋግጡ ማናቸው ተሰትፎዎች ተከብሮ መጠራቱ ቀርቶ፤ በሰላም ጥያቄ ሊያቀርብ የሚሄደውን ዜጋ በጽሞና በማዳመጥ ለቀጣዩ አካል ማስተላለፍ ሲገባ በባሩድ ሩምታ ዜግነት ከነአርማው ሲደበደብ አዬን። ከዚህ ሲዊዝ የተፈጸመው የሰው ልጆች የማይገሰስ መብት ተግባራዊነት ለብራዚላውያን፤ በአሜሪካ ደግሞ ኢትዮጵውያን ላይ የደረሰው በቋሳ የጨቀዬ ግፍና በደል ባልተራራቀ ሰሞናት የተከወነው ትዕይንት ምን ያህል የሰብዕዊ መብት ረገጣ ከሀገር አልፎ የዜጎችን ጉዳይ ይወክላል በተባለው ቆንጽላ ጽ/ቤት እንደ ተፈጸመ የሚያረጋግጥ የሀቅ ማህተም ነው። ለነገሩ ባለፉት ወራቶች አሜሪካን ሀገር ተካሂዶ በነበረው የአንባገነን አፍሪካውያን ዬመሪዎች ጉባኤ የህዝብን ሮሮ ያላደመጠው አካል፤ አሁን በዓይኑ፣ በብሌኑ አይቶ ይፈርድ ዘንድ የሰማዩ ዳኛ የላከው የምፅዓት ቀን ደወል ነው። ኢትዮጵያ አምላክ አላት። – አቅሟ – ኃይሏ  – መመኪያዋ  – መጠጊያዋ ፈጣሪያዋ ነውና።

በሌላ በኩል ውጭ ያለነው ተዘለን እንኳን፤ ሀገር ቤት ያለው ዜጋ በትክክል ለውሳኔው ድምጹን በነፃነት መስጠት ይችላል ወይ ለሚለው በስማ በለው ሳይሆን በ97 የተከወነው ጽልመታዊ አንበገነናዊ ድርጊት ምስክር ነው። የጠቆረው ታሪካችንም አካል ነው። ከአራት አመት በኋላም የአደራ አርበኛው አቶ አንዷለም አራጌ እስር ጨምሮ ከዚህው ስጋት የመነጨ ነበር። ለቀጣዩም ምርጫ ቁርሾን ከዝኖ ገና ከመምጣቱ አስቀድሞ እነ አቶ ሃብታሙ አያሌው፤ አቶ ሺዋስ አሰፋ፤ አቶ ዳንኤል ሺበሺና ጋዜጠኛ አብርሃም ደስታ ሰለባ የሆኑበት ምክንያት ይሄው ነው። ያደላቸው ደግሞ በተሰደዱበት ሀገር መብታቸው ተከብሮ በነፃነት ለወደዱት ድምጽ ሲሰጡ አዬን። ብራዚላውያን እርቀው ቢኖሩም መንግሥታቸው የሚያስባቸው መሆኑ፤ በራሱ በሚኖሩበት ሀገርም ተከብረው እንዲኖሩ ያደርጋቸዋል። አንተ ላጣህ ሌላው ያገልሃል፣ ያቀልሃል ጉዳዩም አይደለም፤ “ባለቤት ያቃለለውን አሞሌ፤ ባለ ዕዳ አይቀበለውም” እንዲሉ። አንተ ለኖረህ ደግሞ ሌላው ይንከባከበሃል – ያሽቃብጥልሃል – ያሸከሽክልሃል። እኛ ኢትዮጵውያን ግን የሁለት ሀገር ስደተኞች ነን። እረኛ አልባ … ምንዱባን …..

አልቀረለትም – ሰንድቅአላማችንም የመከራው ዘመን ታዳሚ ነውና በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሲተኮስበት ታዬ – በባዕድ መሬት። ዜጎችም የነፃነት ጥያቄ ባቀረቡ ተመሳሳይ ዕጣ ገጠማቸው። እርግጥ ነው የጫካው አራዊት ወያኔ በጥርሱ ይዞ በጠላትነት ከፈረጃቸው ዬኢትዮጵያዊነት መግለጫዎች ታላቁ ሰንድቅአላማች ነው። ወያኔ ጫካ በነበረበት ጊዜ ሲሰኘው ሲያቀጥለው፤ ሲያሻው የአሞሌ መቋጠሪያ ሲያደርገው፤ ሲለው ደግሞ የእግሩ ገንባሌ አድርጎ ሳይሰቀጥጠው – ሲጠቀጥቀው፤ ከዚህም ባለፈ ሳይፈሩ፣ ሳያፍሩ በድፍረት ትዕቢተኛው የወያኔ መሥራች መሪው ሄሮድስ መለስ ዜናዊ በአደባባይ “ጨርቅ” እያሉ መሳለቃቸው የጨለማው ታሪካቸው ክፍለ አካል ሆኖ፤ ዛሬ ደግሞ በሌለ ልብጥ አርቲፊሻል መንጣጣት … አንገት – የለሽነት።

ወያኔ ቀድሞውን የተነሳበት ኢትዮጵያዊነትና ኢትዮጵያን ማጥፋት በመሆኑ በዚህ ዙሪያ ያሉ ተቋማትን ካላ ምህረት ነው በተከታታይ ከትክቶና ቀጥቶ ለማምከን የሚታገለው። ዛሬም ቢሆን እዬነጠሉ የእሳት እራት የሆኑ አርበኞቻችን በሰንድቅአላማቸው ላይ የማያወላውል ቁርጠኛ አቋም ያላቸው፤ የማይደራደሩም በመሆናቸው ብቻ ነው።

እዚህው ዘሃበሻ ላይ 8ጊዜ የኢትዮጵያ ሰንድቅዓላማችን እንደተቀያዬር የሚገልጽ ጹሑፍ አንብቤያለሁ። ምን ለማለት እንደሆነ ባይገባኝም፤ አስፈላጊነቱም ለአሁን ጊዜ ምን ያህል እንደሆነ ባይረዳኝም፤ ምን አልባትም ለነገ የጠራ አቋም እንዲያዝ ታስቦበት ሊሆን ስለሚችል ሃቁን ማንጠር ያስፈልጋል። ከወያኔ በፊት በነበረው ጊዜ ሰንድቅዓላማችን ላይ ሌላ የመንግሥት ታካይ ውክል ፍላጎት ቢኖርበትም ሰንድቅዓላማችን በአዋጅ አልታሰረም፤ አልተረሸነም፤ ማዕቀብ አልተጣለበትም፤ አልተቃለለም፤ አልተንቋሸሸም፤ በክፉ ዓይን አልታዬም፤ አልተገላመጠም፤ በወንጀለኝነት ተጠያቂም አልነበረም – አልተገፋም እንዲያውም የሚያበረታታ ተግባር ነበር ሲከወን የኖረው። ክብሩ – ማዕረጉ –  ሙላቱ – ልክ አልነበረውም። ዋቢ ላለው ሀገራዊ ተልዕኮ እራሱ መሪ – ተመራጭ  – አደራጅ – አስተናባሪ – ግንባር ቀደም እንዲሆን ያልታሰረ ንጹህ ነፃነት ነበረው በግርማና በሞገስ ነበር።

በምልሰት የነበረውን ተደማጭነት ሆነ ተቀባይነት ሲገመገም፤ በዬጊዜው ማህሉ ላይ ተጨመረበት የሚበልለት ሰንደቅዓላማ የመንግሥት አካላት በቢሮቸው ከሚያስቀምጡት በስተቀር በዬትኛውም ቦታና ጊዜ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ለመላ ኢትዮጵያ ህዝብ የእትብት ውስጥነት መለያ ረቂቅ መንፈስ የነበረው፤ ለዜጎች የማንነታቸው መግለጫ፣ የሐሤታቸው ማፍኪያ፣ የሃዘናቸው ማስታገሻ – ማጽናኛ፤ እንዲሁም የዕምነታቸው – የአውዳማታቸው ሆነ የባህላቸው አባዎራቸው፤ ዓዕምዳቸው፣ አንጎላቸውና አንገታቸው የአድህኖ ምስላቸው ነበር – የነበረው። ዜጎች የዳር ደንበራቸው ልዩ የክብር ጌጥ አድርገው አምልከውትም ኖረዋል። ይህን በማድረጋቸው ደግሞ አይታሰሩም፤ አይንገላቱም፤ ወይንም አይሰደዱም ወይንም ሰው ሳያይ ሰንደቅዓላማቸውን እንደለበሱ በቂም በቀል አይገደሉም። ሆኖም ተደርጎም አያውቅም። ስለዚህ የዛሬው የበቀል ቅጥቀጣ ምንጩ አንድ ነው ባንዳነት ነው። ኢትዮጵያ በነፃነት ተከብራ መኖሯ፤ ሉዕላዊነቷ ተደንቆ – ደምቆ መኖሩ፤ የአፍሪካ ቀንድ ማዕከል መሆኗ የጎረበጠው የጫካ አራዊት ትናንትም ዛሬም – ነገም ለሰንደቅዓላማችን ጠላትነቱን በዬአጋጣሚው እዬገለጸ ነው።

በምንም ዓይነት መስፈርት በዐጤው ጊዜም ሆነ በዘመን ደረግ የነበረው የሰንድቅዓላማ የመንግሥት የጥበቃና የእንክብካቤ ደረጃ ከባንዳው ወያኔ ጋር ለማነፃፀሪ ማቅረብ በሥጋ የሌለች አንስት ነፍሰጡር መሆን ትችላለች ብሎ የማመን ያህል ነው ለሃቁ የሚርቀው – ለዬትኛውም የማነፃፀሪያው ሆነ ዬማካካሻ ድርድር። … በህግ አምላክ! እንዲህ ከተቀረቀረ መንፈስ ጋር ዬቀደምት ግርማ ሞገስ ከዚህ ጉማማ ዘመን ጋር አይነካካ። ከዚህ ባለፈ እማማ አፍሪካን የነፃነት ወተት አጥትቶ እራሷን ያስቻለ አንቱ ነው – የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ – የቅኔ ሊቃውንቱ። ድንበር አልቦሽ ተወዳጅና ተናፋቂ የበኽረ ነፃነት የጥቁር ዕንቁ አንድምታ ነው ሰንደቅዓላማችን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ።

ይህ ለዚህ ንቁ ትውልድ በእጁ ያለ፤ ክፉና ደግ የሚሰማበት፤ በጎሪጥ የሚታይበት፤ ብሄርተኛ እዬተባለ የሚገለልበትና የሚቀጠቀጥበት በመሆኑ ለቀባሪው አረዱት ይሆናል። ነገ ወያኔ ሊያደርገው የሚችል ቀጣይ ነገር ይኖራል። አንድነታችን እንዲሸረሽር ታስቦ በተዘጋጀው የመርዝ ስሌት ብቀላ ምስል ላይ በህዝብ ድምጽ በጉልበት እንዲጸድቅ ሊያደርገው ይችላል። ማዋጋት – ዕዳ ትቶ ማለፍ የወያኔ ህልሙ ነውና። ባህሪውም ይኼው ነው። ዜጎችን ሰላም መንሳት – ማወክ – መወጠር – መንፈስን ማባካንና ማፈናቀል። ነገር ግን ….  ኢትዮጵውያን ትናንት የሞቱለት ዛሬም የሚሞቱለት ሰንደቅዓላማ ግን መቼውንም ህያው ይሆናል። ይኼው ታሪክ እራሱን ደገመና ደረታቸውን ለጠላት ባሩድ የሰጡ ጀግኖች የወያኔን ምልክት በጀግንነት ከቦታው አወረዱትም። “ … ወደ ኤምባሲው ገብተው የነበሩት ኢትዮጵያውያንም በአሁን ወቅት የኢህአዴግ  መንግስት የሚጠቀምበትን ባለኮከብ ሰንደቅዓላማ በማውረድ የቀድሞውን ታሪካዊ የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ለተወሰነ ጊዜ ሰቅለው ከግቢ እስኪወጡ ማውለብለባቸው በስፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች ጠቁመዋል፡፡ https://addismedia.wordpress.com/tag/usa-ethiopian-embassy-tplf-eprdf/” ነገም ይቀጥላል። የናፈቃቸው፤ ዓይናቸው የራበው በተሰደዱበት ሀገርም ሰንደቅአላማችው ከንክብሩ ሲውለበለብ ማዬት ነበርና በጀግንነት ፈጽመው ቆይታቸውን ቀለማም አደረጉት – የዘመናት አብነታዊ ተቋማት። ኑሩልን – ጀግኖቻችን – ኩራቶቻችን።

ይህን በደማችን ውስጥ የሚንቀለቀለውን የብሄራዊ ስሜት መግለጫ ወያኔ ማምከን ፈጽሞ አይችልም። ደምና ሥጋ ነው ለእኛ ሰንደቅዓላማችን። መንገድ ላይ ፊት ለፊት ሰንደቃችን አጊጠንበት ከወያኔ ተላጣፊዎች ጋር ስንገናኝ እንዴት በመንፈሳቸው ላይ ቤንዚን እንደሚያርከፈክፍ ሰንደቅአላማችን የሚያውቀው – ያውቀዋል። የወያኔ ጀሌ መንፈስ ሰንደቃችን ለብሰን ሲዩ የተለበለበ ግንድ ነው የሚመስሉት። አሁንም ይሄን አጠናክሮ መቀጠል ያስፈልጋል። የተሰወረው ጥቃት አውጪ ቦንብ ነውና። ነገ አዲሱ ትውልድ መታጋል ያለበት ምንም ያልተለጠፈበት ዋጋው ከፍና ዝቅ የማይል ዬኢትዮጵያ ሰንድቅዓላማ ብቻ ድምጽና ነፍሱ መሆኑን በድርጊት ለጠላቱ ማሳወቅ አለበት። የትኛውም ዓይነት መንግሥትና ሥርዓት ይፈጠር ከእንግዲህ ቢያንስ የሰንድቅዓላማችን ህልውና ቋሚ መሆን መቻል አለበት። ከዚህ ለሚወጣ ማናቸውም የሀገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ኃይል ቢሆንም ድምጽን መንፈግ ግዴታችን መሆን ይገባዋል። ብሄራዊ ዓርማችን – ምልክታችን – የወልዮሽ ሃይማኖታችን ንጹሑ አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ብቻ ይሆናል።

ለዚህ ደግሞ አዲሱ ትውልድ ጀምሮታል – ይቀጥላል። ደግሞ ወግ አይቀርም “ሰንድቅዓላማችን ተደፈረ” ተባለ። የት የሚያውቀውን ነው ወያኔ …. ያ … ጨርቅ እያለ ያላገጠበት፤ ያባጫለው፤ ገድለን ቀብረነዋል እያለ የቅራራበት እኮ ነው። ነገር ግን  ማንነት የትም ቦታ በዬትኛውም ሁኔታ ደም ነውና ጎልቶ ጎልብቶ ገኖ ደምቆ – ይጎመራል።

ትናንት የተፈጠሩ፤ ውጪ ሀገርም ተወልደው ያደጉ የተስፋ ዕንቡጦች ዛሬ ሰንድቅአላማቸው የትኛው እንደሆነ ለይተው በሚገባ ያውቁታል። እንዲህ በተመሰጠ – በድንግልና ጥልቅ መንፈስ እንሆ የነገ የተስፋ ልዕልት፤ የሰባዕዊ መብት ተሟጋቿ፤ የፓን አፍሪካኒስት ሩኽ መንፈስ ያልተለያት እመ – ትጉኋን ሳምራዊት ተሰማ ደግና ገዱን መንገድ ሐዋርያ ሆና እዬሰበከች ነው። ድንግልዬ ትጠብቅልን። ውስጧን አንብቡት የኔዎቹ። ሰንደቋ ታቦቷ ነው – ለትውፊት።

ቀደምት አርበኞች እለሞቱም አሉ። ደጎቹ – ደግን ይኼው ተክተዋል። ዓርማቸውን ከፍ አድርጋ አክብራ የምታስከብር አልማዝ እነሆ ሸልሞናል – አምላካችን። ተመስገን! እልፍ ናቸው ዬሰንደቅዐላማቸው ፍቅር ስፍስፍ ዬሚያደርጋቸው – ቀንበጦቻችን። የኢትዮጵያ ሰንደቅ መንፈስ ነው።  መንፈስ አይሸመትም  – አይበደሩትም። አይታመም – ሞትም ድርሽ አይልበትም። የማይለወጥ ቋሚ የደም ማገር ነውና።

የማከብራችሁ ወገኖቼ – በሀገረ አሜሪካ ሰንደቅዓላማችን እንደዛ ባሩድ ሲነጣጠርበት ማዬቱ እራሱ ይሰቅጥጣል። መታሰቡ እራሱ ያንቀጠቅጣል። ዜጎችን ለመግደል ብቻ ታስቦ አልነበረም የተተኮሰው። ሰንደቅዐላማችን ለመግደል – መንፈሱን ለማቁሰል – ቅስሙን በዓለም አደባባይ ለመስበር – ክብሩን ለማዋረድም ታስቦ ነበር። ግን ፍርዱ የሰው ሳይሆን የሰማይ ሆነና ያላመጠውን ሳይውጥ ወንጀል ፈፃሚው ተጠቅልሎ – ተቀጣበት። የቃልኪዳን ውል እንዲህ ይፈርዳል። ሌላም ይኖራል። ዬሰንድቅዓላማ ስጦታው በሰውኛ ፍቺ አይደፈርም – ከቶውንም። ለ1988 ተፈጠረ ለተባለ ልብድ ምስል አለንለት ብሎ አደባባይ መውጣትም – ዝልቦነት ነው። ማፈር- መሸማቀቅ ሲጋባ እንዲህ ጥጋብን አደባባይ ማውጣት የመጨረሻው እራስን ዬማነቅ ትዕይንት ይሆን – ይሆን? የእኔ ውዶች ፍቱት ወይ ተርጉሙት – አቅም ያላችሁ።

ክብረቶቼ ስንብት እናድርግ፤ የሃሳብ ልዩነትን በሰለጠነ መልክ ማስተናገድ ማለፊያ ነው። ስለሆነም በሁለቱም ወገን የታዬው ትክክል ነው የሚሉ ወገኖች ይኖራሉ። ይህ በሃሳብ ላይ አይደለም። በማንነት ላይ ነበር። ነገር ግን ቅኖች ወገኖቼ ልብ ሊሉት የሚገባው አብይ ጉዳይ በማንነት ላይ ውይይትም ድርድርም የለም። ለማንነት አጀንዳ አይያዝለትም። ስለዚህ በነፃነት ሀገር ሃሳብን በሃሳብ የማታገል መርሁ እንዲህ ተግባራዊ ሲሆን ማዬት መልካም ሆኖ ሳለ፤ በሰንደቅአላማችን የጥይት ሩምታ ጉዳይ ግን ቁርጥ ያለ አቋምና ውሳኔ፤ እንዲሁም የጠራ መስመርም መከተል አለብን። እኛ ብቻ እኮነን በቀደምትነት የሰው ልጅ መፈጠሪያ ሆነን የሚያስማማ ብሄራዊ መዝሙር፣ ሰንድቅአላማና ህገ መንግሥት በዓለም የሌለን ህዝቦች። ይህን መራራ ዘመን ለመዋጀት አለን የሚሉ ድርጅቶች ሁሉ የፍላጎታቸው አስኳል ሊያደርጉት ይገባል – አምክንዮ። በተረፈ የፊታችን ሃሙስ Radio Tsegaye 09.10.2014 የተለመደ ዝግጅት ይኖረዋል። የቻላችሁ እ.ኤ.አ ሰዓት አቆጣጠር ከ15 እስከ 16 ሰዓት ላይ፤ ያልቻላችሁ ደግሞ አርኬቡ ላይ ታገኙታለችሁ ማድመጥ ትችላላሁ – ፈቃዳችሁ ከሆነ። ደህና ሁኑልኝ – ኑሩልኝ።

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

ማህበረ-ቅዱሳን አደጋ አንዣቦበታል

$
0
0

መስከረም ፳፰(ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-‹ሕግና ሥርዓት የማይቆጣጠረው ማኅበር ጽንፈኛና አሸባሪ የመሆን ዕድሉ የሰፋ ነው››ሲሉ የኢትዮፐያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ተናሩ።

mahibere-kidusanፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ይህን ያሉት ፡ ‹‹የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደራዊ አስተሳሰብ ማበልፀግ›› በሚል መሪ ቃል ከመስከረም 27 እስከ መስከረም 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መስብሰቢያ አዳራሽ

የተጀመረውን ጉባዔ በከፈቱበት ወቅት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ግልጽ የሆነ መዋቅር ያላት ቢሆንም፤ በቤተ ክርስቲያን ስም የሚደራጁ ማኅበራት፣ ከመዋቅራዊ ቁጥጥር ውጭ በመንቀሳቀስ ሀብትና ንብረት ያከማቹና እያከማቹ

መሆናቸውን የተናገሩት ፓትርያርኩ፣ ሕግና ሥርዓት የማይቆጣጠራቸው ከሆነ አሸባሪ የመሆን ዕድላቸው የሰፋ ነው ማለታቸውን ሪፖርተር ዘግቧል።

ፓትርያርኩ በዚሁ ንግግራቸው በቤተ ክርስቲያን ስም ለሚንቀሳቀሱ ማኅበራት ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም የቤተክርስቲያኗ ልጆች ከቤተ ክርስቲያን መዋቅራዊ ቁጥጥር ውጭ የሚንቀሳቀ ሀብትና ንብረት ማካበት የተከለከለና

በከባድ ወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ይህ ድርጊት እየተስፋፋ ነው፡ያሉት ፓትርያርኩ፣ እየታየ ያለው የማኅበራት ዝንባሌ ሀብት ማካበት፣ ለቤተ ክርስቲያን ብቻ የተፈቀደውን ‹‹አሥራት በኩራት››

ለራሳቸው መሰብሰብ፣ ከቤተ ክርስቲያን ዕውቅና ውጪ የአገር ውስጥና የውጭ ሥራዎችን በሌላቸው ሥልጣን መሥራት- መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ፓትርያርኩ አክለውም፦” ማኅበራቱ በሰበሰቡት ሕገወጥ ሀብት አባቶችን ይከፋፍላሉ፡፡ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ያሾማሉ፣ ያሽራሉ፡፡ የእነሱን ፍላጎት የማይፈጽሙትን ያስፈራራሉ፣ አካሄዳቸው ለቤተ ክርስቲያኗ ጥንካሬና

ህልውና ፍጹም አደጋ ሆኗል”ብለዋል። ፓትርያርኩ በዚሁ ንግግራቸው -በአድባራትና ገዳማት የመልካም አስተዳደር እጦት መንገሡንና ባለፉት አሥርት ዓመታት የምዕመናን ቁጥር መቀነሱንም አመልክተዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ስለማኅበራት በጎ ያልሆነ አሠራርንሲናገሩ ‹‹ማኅበራት›› እያሉ በወል ስም ከመጥራት ባለፈ የማህበራት ስም ባይጠቅሱም፣ በስብሰባው ላይ የነበሩ ከገዳማትና ከአድባራት የተወከሉ

አስተዳዳሪዎችና ጸሐፊዎች ግን ያስገነባውን ሕንፃ ጭምር እየገለጹ ማኅበረ ቅዱሳን መሆኑን በመጥቀስ በማህበሩ ላይ ዕርምጃ እንዲወሰድ መጠይቃቸውን የጋዜጣው ዘገባ አመልክቷል።

የቤተ ክርስቲያኗ ማንኛውም ገቢ እንደ ገንዘብ ሚኒስቴር በአንድ ቋት ሆኖ በቅዱስ ሲኖዶስ ኃላፊነት እንዲመራ ያሣሰቡት አንዳንድ የጉባዔው ተሳታፊዎች፤ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ይቅርታ ጠይቀው ወደ ቀድሞ ቤታቸው

ይመለሱ ሲሉ ተናግረዋል።

Source:: Ethsat

አቡነ ማቲያስ ማህበረ ቅዱሳንን ለጅብ ሊያስበሉት ነው፤ “…አሸባሪ የመሆን ዕድሉ የሰፋ ነው”አሉት

$
0
0

‹‹ሕግና ሥርዓት የማይቆጣጠረው ማኅበር ጽንፈኛና አሸባሪ የመሆን ዕድሉ የሰፋ ነው›› አቡነ ማቲያስ

ከገዳማትና ከአድባራት የተወከሉ አስተዳዳሪዎችና ጸሐፊዎች ግን ሕንፃውን ጭምር እየገለጹ ማኅበረ ቅዱሳን መሆኑን በመጥቀስ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል

በአድባራትና ገዳማት የመልካም አስተዳደር እጦት መንገሡ ተገለጸ ባለፉት አሥርት ዓመታት የምዕመናን ቁጥር ቀንሷል ተብሏል

 

ቤተ ክርስቲያን ግልጽ የሆነ መዋቅር ያላት ቢሆንም በቤተ ክርስቲያን ስም የሚደራጁ ማኅበራት፣ ከመዋቅራዊ ቁጥጥር ውጭ በመንቀሳቀስ ሀብትና ንብረት ያከማቹና እያከማቹ በመሆናቸው፣ ሕግና ሥርዓት የማይቆጣጠራቸው ከሆነ አሸባሪ የመሆን ዕድላቸው የሰፋ መሆኑን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አስታወቁ፡፡

ፓትርያርኩ ይህንን ያስታወቁት ‹‹የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደራዊ አስተሳሰብ ማበልፀግ›› በሚል መሪ ቃል ከመስከረም 27 እስከ መስከረም 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መስብሰቢያ አዳራሽ የተጀመረውን ጉባዔ በከፈቱበት ወቅት ነው፡፡

H_E_Abune_Matiyas_Archbishop_of_Jerusalem_Misa
በቤተ ክርስቲያን ስም የሚንቀሳቀሱ ማኅበራት ብቻ ሳይሆኑ ሌሎችም ከቤተ ክርስቲያን መዋቅራዊ ቁጥጥር ውጭ የሚንቀሳቀስ ሀብትና ንብረት ማካበት የተከለከለና በከባድ ወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ይህ ድርጊት እየተስፋፋ መሆኑን የጠቆሙት ፓትርያርኩ፣ እየታየ ያለው የማኅበራት ዝንባሌ ሀብት ማካበት፣ ለቤተ ክርስቲያን ብቻ የተፈቀደውን ‹‹አሥራት በኩራት›› ለራሳቸው መሰብሰብ፣ ከቤተ ክርስቲያን ዕውቅና ውጪ የአገር ውስጥና የውጭ ሥራዎችን በሌላቸው ሥልጣን እየሠሩ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ፓትርያርኩ እንዳብራሩት፣ ማኅበራቱ በሰበሰቡት ሕገወጥ ሀብት አባቶችን ይከፋፍላሉ፡፡ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ያሾማሉ፣ ያሽራሉ፡፡ እነሱ የሚፈልጉትን የማይፈጽሙትን እያስፈራሩ በመሆናቸው፣ አካሄዳቸው ለቤተ ክርስቲያኗ ጥንካሬና ህልውና ፍጹም አደጋ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በቤተ ክርስቲያን ስም ያለአግባብ ሀብትና ንብረት ያካበተ ማንኛውም ኃይል ባስፈለገ ጊዜ እንቢተኛ በመሆን ቤተ ክርስቲያንን ሊከፋፍል ስለሚችልና በዓለም ላይ ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ ንፁኃንን እየጎዳ ያለውን ትዕይንት ሊያስከትል ስለሚችል፣ ሁሉም የሃይማኖቱ መሪና ተከታይ መታገልና መቃወም እንዳለበት ፓትርያርኩ አሳስበዋል፡፡

ሌላው ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ያነሱት ነጥብ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ቁጥር ባለፉት አሥር ዓመታት ውስጥ መቀነሱን ነው፡፡ ለምሳሌ ያህልም በአዲስ አበባ ሰባት በመቶ፣ በኦሮሚያ አሥር በመቶና በደቡብ 7.8 በመቶ የቀነሰ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የተጠቀሰው ቁጥር እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ አለመሆኑን የገለጹት ፓትርያርኩ፣ የምዕመናኑ ቁጥር መቀነስ በአሉታዊ ጎኑ ሃይማኖታዊና ማኅበራዊ ለውጥ እንደሚያስከትል ጠቁመዋል፡፡ ‹‹ሃይማኖታዊ ተልዕኮአችንን መሠረት አድርገን ብንመለከት ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር የምናቀርበው ሕዝብ እያጣን መሆኑን ያሳያል፤›› ብለዋል፡፡ ምዕመናን ሲቀንሱ የቤተ ክርስቲያን ሀብት እየቀነሰ ስለሚሄድም፣ የሚዘጉ አብያተ ቤተ ክርስቲያናትም እየበዙ እንደሚሃዱ አክለዋል፡፡

የቤተ ክርስቲያንና ጥንታዊ እሴቶችም በአገር ደረጃ የነበራቸው ጠቀሜታ እየቀነሰ ከሄደ፣ የሃይማኖቱና የአገሪቱ መሠረታዊና ማኅበራዊ እሴቶች እንደሚጎዱ የጠቆሙት ፓትርያርኩ ባህሉ ከተጎዳ ጭካኔ፣ ስግብግብነት፣ ስንፍናና ወንጀል እንደሚበዙ ገልጸዋል፡፡ ፈሪኃ እግዚአብሔር ከመቀነሱና ከመጥፋቱም በተጨማሪ የትውልዱ ሥነ ምግባር ተጎድቶ የተለየ አደጋ እንደሚያስከትልም አክለዋል፡፡

አንዳንድ ሰዎች ችግሮችን ግልጽ በማድረግ ውይይት ለማድረግ ሲጠየቁ፣ ‹‹ሌሎች ሃይማኖቶች በእኛ ላይ ሊዘባበቱ ይችላሉና ዝም ይሻላል ብለው ይመክራሉ፤›› ያሉት ፓትርያርኩ፣ ዝም ማለት በመመካከር ሊገኝ የሚችለውን መፍትሔ እንደሚያሳጣ፣ ለምዕመናንና ለሕዝብ የሚሰጠው የተሻሻለ አገልግሎት እንዳይኖር እንደሚያደርግ፣ የቤተ ክርስቲያኗ አስተዳደራዊ ሥራ በዘመኑ ሥልት እንዳይመራና ሃይማኖቱ እንዳይስፋፋ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡ በማከልም በዚህ ዘመን ማናቸውም የሚደረግ ነገር ሁሉ ለሕዝብ ያልተደበቀና ምዕመናን በየቀኑ እያዩት ያለ ጉዳይ በመሆኑ፣ ‹‹ዝም እንድንል የሚመክሩን የቤተ ክርስቲያኗን መሻሻልና መጠናከር የማይፈልጉ ወይም የችግሩን አሳሳቢነት ያልተረዱ ናቸው፤›› ብለዋል፡፡

በአድባራት፣ በገዳማትና በቤተ ክህነት ጭምር ብልሹ አሠራር መስፈኑን የሚያሳይ በሁለት ሳምንት ብቻ ከአምስት በላይ ከሚሆኑ አድባራትና ገዳማት የተውጣጡ ምዕመናንና ካህናት በሠልፍ ወደሳቸው መምጣታቸው ማሳያ መሆናቸውን የተናገሩት ፓትርያርኩ፣ መደለያ (ጉቦ) በመስጠት ፍትሕ እንዲጓደል ማድረግ፣ በዘር፣ በአካባቢ በመደራጀት ንፁኃንን መበደልና ያልደከሙበትን ሀብት ያለአግባብ ማባከን ትምህርተ ወንጌልን የሚፃረር ተግባር መፈጸም በመሆኑ፣ ሁሉም ሊዋጋው የሚገባ ተግባር መሆኑን አሳስበዋል፡፡

በቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸውን ኃላፊነት ተጠቅመው ለራሳቸው ጥቅም የሚሯሯጡ አንዳንድ ሰዎች መኖራቸውን የገለጹት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ በአንዳንድ ቦታ ብቻ ሳይሆን በመዋቅር ውስጥ እንደ ሰንሰለት ተያይዘው ለራሳቸው ጥቅም የሚሠሩ ግለሰቦች መበራከታቸው፣ የላቀ መንፈሳዊ ተግባር ለሚጠብቁ ምዕመናን ክፉኛ የመንፈስ ስብራት እየደረሰባቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ይህንንና ሌሎች ችግሮችንም ከምዕመናኑ ጋር በመተባበር በተለይ ከቤተ ክርስቲያኗ አገልጋዮች ጋር ዓመቱን ሙሉ በሚኖረው ውይይትና ምክክር ችግሩ ሊፈታ እንደሚችል ያላቸውን እምነት ተናግረዋል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ስለማኅበራት በጎ ያልሆነ አሠራርን ሲናገሩ ‹‹ማኅበራት›› እያሉ በወል ስም ከመጥራት ባለፈ ሙሉ ስም ባይጠቅሱም፣ ከገዳማትና ከአድባራት የተወከሉ አስተዳዳሪዎችና ጸሐፊዎች ግን ሕንፃውን ጭምር እየገለጹ ማኅበረ ቅዱሳን መሆኑን በመጥቀስ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያኗ ማንኛውም ገቢ እንደ ገንዘብ ሚኒስቴር በአንድ ቋት ሆኖ በቅዱስ ሲኖዶስ ኃላፊነት እንዲመራ ጠይቀዋል፡፡ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ይቅርታ ጠይቀው ወደ ቀድሞ ቤታቸው እንዲመለሱም እንዲሁ ጠይቀዋል፡፡

ምንጭ፡ ሪፖርተር ጋዜጣ

Health: ከቤት እንስሶቻችን የሚይዙንን ጥገኛ ተህዋስያን (Parasites) እንዴት ማወቅና መከላከል ይቻላል?

$
0
0

ከዶ/ር ዓብይ ዓይናለም

እንስሳትን በተለይም ውሻና ድመትን ወይ ቤት ለማስጠበቅ አሊያም አይጦችን ለማባረር አለፍ ሲልም ደግሞ በሳሎናችን እንደ ጌጥ ማሳደግ የተለመደ ነው፡፡ በአብዛኛው የእንስሳት ባለቤቶች ዘንድ ግን እነዚህ እንስሶች ሊያስተላልፉብን ስለሚችሉት የበሽታዎች መጠንና ስፋት እንዲሁም ስለ ጉዳቶቹ ብዙም አይታወቅም፡፡ ለዛሬ የምናያቸው ከውሾቻችንና ከድመቶች ወደ ሰዎች የሚተላለፉ የጥገኛ ተህዋሳት በሽታዎችን ይሆናል፡፡
pets
ከእንስሳት ወደ ሰው ከሚተላለፉት የጥገኛ በሽታዎች መካከል ዋነኞቹ የመንጠቅ ትል (Hook worm) እና የወስፋት (Ascarids) ናቸው፡፡ ውሾችን በአብዛኛው የሚያጠቋቸው የአስካሪስ ዝርያዎች (Toxocara canis) ሲባሉ ድመቶችን የሚያጠቋቸው ደግሞ Toxocara cati በመባል ይታወቃሉ፡፡ ሁለቱንም የቤት እንስሶች በማጥቃት የሚታወቀው የመንጠቆ ትል ደግሞ በሳይንሳዊ አጠራሩ አንኪሎስቶመም (Ancylostomum) በመባል ይታወቃል፡፡
እነዚህ የወስፋትና የመንጠቆ ጥገኞች በሰው ላይ የምግብና የደም ሽሚያ በማድረግ ተጠቂውን ለተለያዩ ቀውሶች የሚያጋልጡት ሲሆን የሆድ ህመም ከመፍጠራቸውም በተጨማሪ በተለይ በህፃናት ላይ ያላደጉትን እንጭጮቻቸው (Larva) በቆዳ ስርና ወደ ተለያዩ የሰውነት ክፍሎች በመስደድ ተጨማሪ ጉዳት ያደርሳሉ፡፡

የወስፋት ትል (Ascaris)

በውሾ ላይ የአስካሪስ እንቁላሎች በእናትየዋ ማህፀን በኩል አድርገው ለቡችሎቹ ከመድረሳቸውም በላይ እናቲቱ ጡቷን በምታጠባበትም ወቅት ለቡችሎቹ ልታስተላልፍ ትችላለች፡፡ በተቃራኒው የድመት ግልገሎች በበሽታው ሊያዙ የሚችሉት ወይ ከእናትየው ጡት ሲጠቡ አሊያም አካባቢያቸው በጥገኞቹ እንቁላል ከተበከለ ብቻ ነው፡፡
ሰዎች በእነዚህ በሽታዎች ከተያዙም የእነዚህ ጥገኞች እንጭጭ (Larvae) በሰውነት ውስጥ በመዘዋወር የተለያዩ የሰውነት ክፍሎችን በመጉዳት ከጥቅም ውጪ ሊያደርጋቸው አሊያም ደግሞ በአንጀት ውስጥ በሚኖራቸው ቆይታ ከፍተኛ የሆነ የህመም ስሜት ሊያመጡበት ይችላል፡፡ አንዳንዴም አለፍ ሲልም ለህይወትም ሊያሰገኑ የሚችሉባቸው አጋጣሚዎች ይኖራሉ፡፡ በእነዚህ በሽታዎች ተይዞ ተገቢውን ህክምና ያላገኘ ሰው ደግሞ አካባቢውን በጥገኞቹ እንቁላል መልሶ በመበከል በተጨማሪ የበሽታዎቹ መፈጠር ትልቅ አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡

የመንጠቆ ትል (Hook Worm)

የውሻ ቡችሎችም ሆኑ የድመት ግልገሎች በዚህ ጥገኛ ተህዋስ የመጠቃት እድሉ አላቸው፡፡ ይህ ጥገኛ ተህዋስ ከምግብ ጋር አብረው ሲመገቡት አልያም ደግሞ ቆዳቸውን በመብሳት ወደ ሰውነታቸው አሊያም ደግሞ ቆዳቸውን በመብሳት ወደ ሰውነታቸው ሊገባ ይችላል፡፡ የመንጠቆ ትል አንዴ ከእንስሶቹ ሰውነት ከገባ በኋላ መጠኑ እጅግ የበዛ ደም በመምጠጥ ሰውነታቸውን ለደም ማነስ ይዳርገዋል፡፡ በተለይም በዚህ በሽታ የተያዙት ዕድሜያቸው ገና የሆኑ ቡችሎች ከሆኑ ከፍተኛ የሆነ ደም በመምጠጥ ለሞት ሊያበቃቸው ይችላል፡፡ የእነዚህ ሁለት ጥገኛ ተህዋስያን በእንስሶች ውስጥ እጅግ የተለመደ መሆኑና ብዙም ካልዳበረው እንስሳትን የማሳከም ባህል ጋር ተደማምሮ እነዚህን ተላላፊ በሽታዎች በአምክሮ እንድንመለከታቸው ያደርገናል፡፡ በሌሎች አገራት በዚሁ ዙሪያ የተደረጉ አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያሳዩትም ውሾችን በተለይም ቡችሎችን የሚያሳድጉ ግለሰቦች ላይ የእነዚህ በሽታዎች መከሰት እጅግ ከፍተኛ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ የህፃናት ከውሾች ጋር የሚኖራቸው የመጫወት ልማድና ቀረቤታ አንጻርም ከአዋቂዎቹ በበለጠ በእነዚህ በሽታዎች እንዲጠቁ ያደርጋቸዋል፡፡
ከእንስሶቹ ሰገራ ጋር ተቀላቅሎ የሚወጣውን እንቁላል በሆነ አጋጣሚ ወደ ሰዎች አፍ ከገባ በቀጥታ ወደ አንጀት በመውረድ ይፈለፈላል፡፡ በዚያም በዛ ያሉ እንጭጮች (Larvae) ይፈጠራል፡፡ እነዚህ ላርቫዎችም ወደ ተለያዩ የሰውነት ክፍሎች በመጓዝ ‹‹ቪዘራል ላርቫ ማይግራንስ›› (visceral larva migrans) የሚባል በሽታ ያስከትላሉ፡፡ ይህ ሁኔታ በሰዎች ላይ ሲከሰትም የጉዳቱ መጠን የሚለካው በተጎዱት የሰውነት ክፍሎች መጠን ይሆናል፡፡ በአብዛኛው ይህ በሽታ ‹‹Soft organs›› የሚባሉትንና እንደ አይን፣ አዕምሮ፣ ጉበትና ሳንባን የሚያጠቃ ሲሆን በምላሹም ቋሚ የሆነና የማይድኑ የአይን፣ የነርቭ ወይም የሌላ ችግር ያስከትላል፡፡
የመንጠቆ ትልም በሰዎች ዘንድ ልክ እንደ ወስፋት በአፍ ውስጥ በመግባት በሽታን የሚያመጣ ሲሆን ከዛ በተጨማሪ ግን በቀጥታ ቆዳን በመብሳትም ጭምር በበሽታው ሊያሲዝ ይችላል፡፡ ይኼኛ 㜎ፅገኛ 㗹㜎ነጽ ቆዳን በሽጾ በሚገባበጽ ጊዜ በቆዳ ሽር ረጅም መንገድን 㜎ሚጓዝ በመሆኑ ‹‹ኩታኒየስ ላርቫ ማይግራንስ›› (Cutancous larva migrans) በመባል ይታወቃል፡፡ የዚህ አይነት የቆዳ ስር የላርቫ እንቅስቃሴ በተጠቂው ግለሰብ ላይ በተከታታይ የማሳከክ ፀባይ ያለው ሲሆን ቀጥ ያለ መስመር ያላቸውና ያመረቀዙ ቁስሎችንም የላርቫውን መንገድ ተከትለው እንዲወጡ ያደርጋል፡፡ አንዳንዴ ወደ ውስጠኞቹ የአካላችን ክፍሎች ድረስ በመዝለቅ በተለያዩ የአካል ክፍሎቻችን ላይ ተፅዕኖዎችን መፍጠር የሚችል ሲሆን አንጀት ድረስ በመዝለቅ አንጀታችን ላይ የመቆጣት ስሜት እንዲፈጠር ማድረግ ይችላል፡፡

መከላከያዎቹ

ከውሻና ከድመት ተነስተው ሰዎችን የሚያጠቁት አብዛኞቹ በሽታዎች በተለይም ከላይ የተጠቀሱት የጥገኛ ተህዋስያን በሽታዎች በቀላሉ የግል ንፅህናን በመጠበቅ፣ ውሻና ድምቶቻችንን ተገቢውን የሆነ ፀረ ተህዋስያን መድሃኒቶችን በፕሮግራም በተከታታይ እንዲያገኙ በማድረግና ለድመቶቻችን መፀዳጃ የምናስቀምጣቸውን አሸዋ የተሞሉ ካርቶኖች ሰዎች በተለይም ህፃናት የማይደርሱበት ቦታ በማስቀመጥ መከላከል ይቻላል፡፡ ሌላው ደግሞ ተገቢ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው የውሻና የድመትን ሰገራ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው የውሻና የድመትን ሰገራ በአግባቡ ማስወገድ ነው፡፡ ይህም ከጊዜ ብዛት በአካባቢ ላይ ተቀምጦ በዝናብና በንፋስ አካባቢውን የበለጠ እንዳይበክለው ይረዳል፡፡
አንዲት ሴት የአስካሪስ (ወስፋት) ጥገኛ ትል በቀን እስከ 100,000 እንቁላል የምትጥል ሲሆን በዚህ በሽታ የተጠቁ ውሾች ባሉበት አካባቢ ምን ያህል እንቁላል ሊኖር እንደሚችል ግምቱን ለአንባቢ ትቼዋለሁ፡፡ እነዚህ እንቁላሎች አንዴ አካባቢውን ከበከሉት ለዓመታት በዛው የሚቆዩ በመሆኑ በአካባቢው የሚገኙ ሰዎችን ለረጅም ጊዜ የጉዳቱ ሰለባ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡ ቡችሎች፣ የድመት ግልገሎች እርጉዝ እና የሚያጠቡ እንስሶች በእነዚህ ጥገኛ ተህዋስያን የመጠቃት ዕድላቸው ከፍተኛ በመሆኑና አካባቢንም በስፋት የሚበክሉት እነሱው በመሆናቸው የፀረ ጥገኛ ተህዋስያን ህክምናው በእነዚሁ እንስሳት ላይ ቢደረግ የተሻለ ውጤት ማግኘት ይቻላል፡፡ ለዚህ ደግሞ የእንስሳት ሐኪሞች አስተዋፅኦ እጅግ የጎላ በመሆኑ ለደንበኞቻቸው ተገቢውን የምክርና የማሳወቅ ስራ መስራት ይኖርባቸዋል፡፡

ልዩ የእራት ምሽት በቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ ሚኒሶታ


ጃዋሪዝም (የማምታታት ፖለቲካ) በጌታቸው ሺፈራው

$
0
0

‹‹(ጠባብ) ብሄርተኝነት ልክ እንደ ርካሽ መጠጥ ነው፡፡ መጀመሪያ እንድትጠጣው ይገፋህና ያሰክርሃል፡፡ ቀጥሎ አይንህን ያውርሃል፡፡ ከዛም ይገድልሃል፡፡›› ዳን ፍሪድ

በጌታቸው ሺፈራው

(የግል አስተያየት)

Jawarጃዋር መሃመድ ከአመታት በፊት ከማደንቃቸው ኢትዮጵያዊ አክቲቪስቶች መካከል አንዱ ነበር፡፡ በተለይ ይህ ወጣት ከጥቂት አመታት በፊት እነ በረከት ስምኦንን አልጀዚራ ላይ ሲያፋጥጣቸው ሳይ አድናቆቴ ከፍ ብሎ ነበር፡፡ በዚህ ወቅት ጃዋር ወደ ሶማሊያ ዘው ብሎ ስለገባው ሰራዊት፣ ቋንቋ ሳይለይ በየትኛውም ኢትዮጵያዊ ላይ የሚደርሰውን በደል ሽንጡን ገትሮ መከራከሩ ይታወሳል፡፡ ግን ምን ያደርጋል ይህ አቋሙ እንደተጠበቀው ሊዘልቅ አልቻለም፡፡ መሃል ላይ የ‹‹እኛ እና እነሱ›› ብልሹ ፖለቲካ ሰለባ ሆነ፡፡

በተለይ በአንድ ወቅት አልጀዚራ ላይ ቀርቦ ‹‹በቅድሚያ ኦሮሞ ነኝ›› ካለ በኋላ የፖለቲካ አቋሙ እየተንሸራተተ ሜንጫን እንደ ህጋዊ ነገር ማንሳት ውስጥ ገባ፡፡ አንዴ ‹‹ኢትዮጵያዊ ሙስሊም›› ሆኖ የኦሮሞ ሙስሊሞች ነጻነት ለሌላው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ነጻነትም ወሳኝ ነው ሲል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክርስቲያኑን ኦሮሞ በሜንጫ አንገቱን ስለመቅላት ይሰብካል፡፡ (ይህን መረጃ የተቀነባበረ ነው የሚል መረጃ ያቅርብ)፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ክርስቲያኑን ኦሮምኛ ተናጋሪም ጭምር ወክሎ ‹‹ቅድሙያ ኦሮሞ ነኝ›› አለ፡፡

ከዚህ ውጣ ውረድ በኋላ ጃዋር በቅርቡ ከ‹‹ኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ›› ጋር ቃለ መጠይቅ አድርጓል፡፡ በቃለ መጠይቁ እስካሁን አሉ የሚላቸውን ብዥታዎች ለማጥራትና አቋሞቹንም ለማስረገጥ በሚመስል መልኩ የቀረበ ይመስላል፡፡ በዚህ ቃለ መጠይቅ ጃዋር ከዛ በፊት እንዳደረጋቸው አነጋጋሪ ነገሮች ባይኖሩትም ቃለ መጠይቁ በሙሉ ‹‹ምክንያታዊ ናቸው›› በሚላቸው ምክንያት አልባ የማምታታት ክርክሮች የተሞሉ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ፡፡

በቃለ መጠይቁ አልጀዚራ ላይ ‹‹መጀመሪያ ኦሮሞ ነኝ›› ያለበትን አቋሙን የሚያጠናክርበት ነው፡፡ ‹‹በልጅነቴ ነው በፖለቲካው ተጠምቄ ያደኩት›› የሚለው ጃዋር ‹‹ከተወለድኩበት ጊዜ ጀምሮ እስከምሞትበት ጊዜ ድረስ ከምንም ከማን በላይ ራሴን እንደ ኦሮሞ ነው የማያው፡፡›› ሲል በ‹‹ማንነቱ›› ሁኔታ ላይ ይደመድማል፡፡ ግን በዚሁ ቃለ መጠይቅም ቢሆን ከአንድ አቋም ወደ ሌላ አቋም ሲዘል ታይቷል፡፡

ጋዜጠኛው ‹‹ኦሮሞ ፈርስት›› የሚለው ጉዳይ ከመነሳቱ በፊት ኢትዮጵያዊ በሆኑ አጀንዳዎች ይሳተፍ እንደነበር በመግለጽ ከዛ በኋላ አቋም መቀየር አለመቀየሩን ሲጠይቀው ‹‹አልቀየርኩም›› ይላል፡፡ መልሶ ደግሞ ‹‹አየህ! ከ2008፣ 2009 በኋላ ‹ኮንሸስ› የሆነ ምርጫ አድርጌያለሁ፡፡ በተለይ ከአማራ ልሂቃን ጋር በመገናኘት ለእነሱ ስለ ኦሮሞ ህዝብ ትግል በማስረዳት ከእነሱ ጋር አብሮ ለመስራት ይቻላል የሚል እምነት ነበረኝ፡፡ የአማራ ልሂቃን በኦሮሞ ትግል ላይ ያላቸው አመለካከት በጣም የሚያስደነግጥና በጣም የሚያስፈራ ነበር፡፡ በትምህርት ጥናቴም ሆነ ባለኝ ቀረቤት ችግሩ ምንድን ነው ብየ ሳስበው ምን አልባት ካለማወቅ (ኢግኖራስን) የመነጨ ነው የሚል ነበር፡፡ ሁለቱንም አካል ወደ መሃል በማምጣል አብሮ መስራት ይቻላል በሚል አምስት አመት ያህል ነው የሰራሁት፡፡ ነገር ግን ያለው ችግር የግዝብተኝነት (አሮጋንስ) ችግር እንዳለ ተረዳሁ፡፡ ኦሮሞ ፈርስት የሚለው ከመምጣቱ በፊት ስርቤይ አድርጌ ነበር፡፡ …27 ያህል ሰዎችን ደውየ 1 ወይም 2 ብቻ ናቸው የተቀበሉት፡፡ እንዲሁም የኦሮሞ ትግል እየተዳከመ በመጣ ቁጥር ያላቸው ንቀት እየተጠናረ ሄደ›› በሚል አቋሙን መቼ እንደቀየረ ለማስገንዘብ ሲጥር ‹‹ከተወለድኩ ጀምሮ እስከሞት ድረስ ኦሮሞ ነኝ›› የሚለው የ‹‹አሁኑ›› አቋሙንም ራሱ መልሶ ይከራከረዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ሌላ አቋሙን የቀየረበት ምክንያት እንዳለው ጃዋር እንዲህ ያስረዳል፡፡ ‹‹…በግብጽ የሚገኙ የኦሮሞ ስደተኞች በአባይ ጉዳይ ላይ ኢትዮጵያና ግብጽ ባለባቸው ችግር ጥቃት ሲደርስባቸው ‹‹እኛ ኦሮሞዎች ነን፡፡ ከኢትጵያ መንግስት ጋር ምንም ትስስር የለንም ሲሉ እንዴት አባታችሁ ኦሮሞዎች ነን ትላላችሁ የሚል በጣም አጸያፊ የሆነ የሚዲያ ዘመቻ ተጀመረባቸው፡፡ ያ ለእኔ ቀይ መስመሩን ያለፉበት እንደሆነና ……በዚህም በማንነታችን ላይ የተነጣጠረ ጥቃት ነው ወደሚል ገባሁ›› ይለናል፡፡ እንደ ጃዋር ከሆነ ግብጽ ውስጥ አማርኛ፣ ትግርኛ፣ ሲዳምኛ….. ተናጋሪዎች የሉም፡፡ አሊያም ጥቃት አልደረሰባቸውም፡፡ ወይንም ደግሞ ነገ ጃዋር ቆሜለታለሁ በሚለው ኦሮሞነታቸው ግብጾች ጥቃት የሚያደርሱባቸው ሲሆን ‹‹እኛ ኦሮሞዎች አይደለንም፣ ከኦሮሞ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የለንም፡፡›› ቢሉ ትክክል ናቸው እንደማለት ነው፡፡

በዚህ ቃለ መጠይቅ ጃዋር ተራ የሀሳብና የአመክኖ ማምታታት ብቻ አይደለም የሚታይበት፡፡ አንዴ መለስ ዜናዊ፣ ሌላ ጊዜ ኦነግ፣ አሊያም ኦህዴድ የያዙትን አቋም አቋሙ አድር ሲከራከርበት፣ ‹‹እኛ›› እያለ ሲገልጽ ተስተውሏል፡፡

ለአብነት ያህል 27 ያህል የ‹‹አማራ ልሂቃንን›› አነጋግሬ አገኘሁት የሚለውን መደምደሚያ ሲገልጽ ነፍጠናውን አከርካሪው ሰብረነዋል የሚለውን አቶ መለስ አቋም በግልጽ እንደተጋራ ይታያል፡፡ ጃዋር ‹‹ይህን አሮጋንስ ማስተካከል የሚቻለው … ቀኝ ዘመሙን የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት አከርካሪውን በመስበር እጅ ማሰጠት ነው፡፡ ያ ፖለቲካ እንደማይሰራ ወደ ‹ኮምፕሊት ፖለቲካል ባንክራፕሲ› ማስገባት ግዴታ ነው በሚለው መደምደሚያ ደርሼ ነበር፡፡›› ይላል፡፡ ይህኔ ጃዋር መለስን መለስን ነው የሚመስለው፡፡

ኦህዴድ ከገዥው ቡድን ጋር ተባብሮ የኦሮሞን ህዝብ እየበደለ ስለመሆኑ ለተነሳለት ጥያቄ ጃዋር ኦህዴድን ምንም አቅም የሌለው አድርጎ ይገልጸዋል፡፡ መልሶ ደግሞ ለህወሓት ፈታኙ ኦህዴድ ነው እያለ ያምታታል፡፡ ጃዋር መጀመሪያ ‹‹ለእኔ የኦህዴድ አመራሮችም ሆነ አባላት በአንድ ፋብሪካ የሚሰሩ የፋብሪካ ዩኒየን ያህል ጉልበት የሌላቸውና የማይፈቀድላቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ከተፈጠረበት ጊዜ ድረስ እስካሁን ድረስ ምንም አይነት ድርጅታዊ ስብዕና የሌለው ድርጅት ነው፡፡›› በማለት ከምንም የማይገባ፣ ለምንም የማይሆን አቅመ ቢስ ያደርገዋል፡፡

ምንም አቅም የላቸውም ያለውን ተመልሶ ‹‹..ህወሓት እንደፈለገው ኦህዴድ ቡችላ የሚሆንለት አይደለም፡፡ ምክንያቱም ብዙ ያልነቁት በእድሜ እየገፉ በሄዱ ቁጥር፣ ከኦነግ ጋርም ለመሻማት የተማሩትን ወደ ድርጅቱ እየከተተ በሄደ ቁጥር፣ ኦህዴድ እንደ ድርጅት ባይጠናከርም ግለሰቦች በተቻለ መጠን የህዝቡን መብት ለማስጠበቅ እየተንቀሳቀሱ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ እንዲያውም በአሁኑ ወቅት ለህወሓት ከማንም በላይ አስፈሪው ኦህዴድ ሆኖ ያለበትና ባለፉት ሁለት አመታት የምናየው ዳይናሚክስ ከፍተኛ አደጋ እየፈጠሩበት እንዳለ ነው የምናየው፡፡›› በማለት በቅጽበት ኦህዴድን ከአነስተኛ ፋብሪካ ዩኒየንነት ወደ ግዙፍና አስፈሪ ፓርቲነት ያሳድገዋል፡፡

ጃዋር መጀመሪያ ‹‹እንደ ድርጅት አልቆጥረውም፤ አቅመ ቢስ ነው፡፡›› ስላለው ኦህዴድ ይቀጥላል፡፡ ‹‹ያ ብቻ አይደለም የተማሩ ኦሮሞዎችን በግዳጅ ወደ ቢሮክራሲው አስገብቷል፡፡ እነዚህ ግለሰቦች ቢያንስ ከስርዓቱ ጋር እምብይ ማለት ቢያቅታቸው ‹አክቲቭሊ› ህዝቡን መበደል እያደረሱ አይደለም፡፡ …..ከዚህም የተነሳ በኦነግ የተጀመሩ ብዙ ፕሮጀክቶችን ወደማጠናቀቀ እየደረሱ ነው ያለው›› በማለት ኦህዴድን የኦነግ ‹‹ራዕይ አስቀጣይ›› ያደርገዋል፡፡ ይፈጽማል ከሚባለው ኃጥያት ነጻ ሊያወጣው ይሞክራል፡፡

ጃዋር ከአንድ የፋብሪካ ማህበር አይሻሉም የሚላቸውን ኦህዴዶች እንደገና ሲያማካሻቸው ጋዜጠኛው ‹‹ስለዚህ የኦህዴድ መኖር አስፈላጊ ነው?›› ብሎ ይጠይቃል፡፡ ጃዋር ግን አሁንም ያምታታል፡፡ ‹‹አይደለም!›› ይላል፡፡ ግን ደግሞ ስለ ኦህዴድ አስፈላጊነት እንዲህ ይገልጻል፡፡ ‹‹በአሁኑ ወቅት ወደ 90 በመቶ የሚሆነው የኦሮሞ ልሂቃን ኦህዴድ ውስጥ ነው ያለው፡፡ ስለዚህ ቀጣዩ የኦሮሚያ እጣ ፈንታ በእነሱ እጅ ነው ያለው፡፡›› በማለት መኖሩ አስለላጊ አይደለም የተባለው ኦህዴድ የኦሮሚያ እጣ ፈንታ ሆኖት ያርፋል፡፡ ጃዋሪዝም እንዲህ በደቂቃዎች አቋምን የመቀየር፣ የመቀያየር፣ የማምታታት ፖለቲካ ነው!

ይህ እንግዲህ ጃዋር ነው፣ ፖለቲካው ደግሞ ጃዋሪዝም፡፡ ስለዚህ አሁንም ማምታታቱን ይቀጥላል፡፡ እናም በአዲስ አበባ ‹‹መሪ እቅድ ወይም ማስተር ፕላን›› ላይ ለተነሳው ተቃውሞ ኦህዴዶች አሉበት እንደሚባል ጋዜጠኛው ሲያስታውሰው ‹‹ማንኛውም ኦሮሞ ኦህዴድም ሆነ ኦነግ ‹‹ማንነት፣ ኦሮሞ የሚባል ነገርና አዲስ አበባ ጉዳይ አንድ ናቸው›› በማለት ኦህዴድን ከማህበር ወደ ለህዝብ እንደሚያስብና አላማ ያለው የፖለቲካ ድርጅት ያደርገዋል፡፡ በአብዛኛው የቃለ መጠይቅ ክፍል መጀመሪያ ላይ ‹‹የዩኒየን አቅም ያህል የሌላቸው›› ያላቸውን ኦህዴዶች ያሞገሰበት ነው፡፡ ‹‹የዛሬ 9 አመት አካባቢ ዋና ከተማው ወደ አዳማ ሲዛወር ኦህዴድ ከፍተኛ ተቃውሞ ማድረጉን፤ ወደ ዋና ከተማውን አዲስ አበባ ማስመለሳቸውን በመግለጽ ‹‹የዩኒየን ያህል አቅም የላቸውም፣ የፖለቲካ ድርጅትም አይደሉም ስላላቸው መወድስ ያቀርባል፡፡

አሁን በአዲስ አበባ በተፈጠረው ችግር ደግሞ ‹‹በኢህዴድ ውስጥ አንድም ልዩነት ሳይፈጠር በአመራሩ በአንድ አቋም የተቃወሙበት ነበር፡፡ በግልጽ የህወሓትን ሰዎች ተቃውመዋቸዋል፡፡ በህወሓትና በኦህዴድ ጉዳይ ላይ በዚህ ጉዳይ ላይ የነበረውን ልዩነት ከአሁን ቀደም ኖሮ አያውቅም፡፡ ከዚያ አልፎ ያን ተቃውሞ ህዝቡ እንዲያውቀው በቴሊቪዝን አስተላልፈዋል፡፡ ይህን በማድረጋቸው ብዙ ሰዎች ለስራቸውም፣ ለህይወታቸውም ለቤተሰቦቻቸውም ራሳቸውን አደጋ ላይ አጋልጠዋል፡፡ ወጣቱም እነሱን ተከትሎ ነው ወደ ትግል የገባው›› በሚል የትግሉ አንቀሳቃሽ ሞተሮች፣ ነጻ አውጭዎች ያደርጋቸዋል፡፡

‹‹በኦህዴድ ውስጥ እከሌን እናጥቃ እከሌን እንግደል ቢሉ የባሰ ችግር ውስጥ ስለሚገቡ እስካሁን እየተፋጠጡ፣ በተቻለ መጠን ኢህዴዶችን በሁለት ከፍለው እያጋጩ ለማዳከም ሙከራ እያደረጉ ነው ያሉት፡፡ ባለፈው ሳምንት ሁለት፤ ሶስት ስብሰባ ተደርጎ ኦህዴዶች በአንድ አቋም ነው ተስማምተው የወጡት፡፡ እናም (ህወሓቶች) የተሳካላቸው አይመስለኝም፡፡›› በማለት ከጠንካራው ኦህዴድ ጎን ሆኖ ህወሓት አቅመ ቢስ እንደሆነ ያወራል፡፡ መቸም መጀመሪያ ላይ ‹‹የዩኒየንን ያህል አቅም የለውም የተባለው ድርጅትና ይህኛው ኦህዴድ በአንድ ሰው፣ ደግሞም በአንድ ቃለ መጠይቅ ላይ፣ በሴኮንድና ደቂቃዎች ልዩነት የተነሳ መከራከሪያ ነው ብሎ ለማመን ይከብዳል፡፡ ግን የሆነው ይህ ነው፡፡ ምክንያቱም ፖለቲካው ማምታታት ነው፡፡ ጃዋሪዝም!

ጃዋር መጀመሪያ ላይ ‹‹አሽከር›› አድርጎ የሚያቀርባቸው ኦህዴዶች ወደ መጨረሻ አናብስት ይሆናሉ፡፡ እነዚህን ‹‹አናብስቶች›› የእራሱ አድርጎ ስለሚቆጥራቸው ኦህዴድን ሰራው የሚለውን ሁሉ ‹‹እኛ እንዲህ አድርገን›› እያለ ይገልጸዋል፡፡ ኦህዴድን እቃወማለሁ እያለ ኦህዴድ ሆኖ (እኛ እያለ) ኦህዴድ ስኬቴ ስለሚለው ‹‹ስኬት›› ይናገራል፡፡ ኦህዴድ አሰራኋቸው የሚላቸውን መሰረተ ልማቶች ‹‹የእኛ›› ሲል አፍለኛ የኦህዴድ ካድሬ ይመስላል፡፡ እንዲህ! ‹‹በተጨባጭ ያሳየነውም ይህንኑ ነው፡፡…….ህወሓት እምብይ እያለ የኦሮሞ ልሂቃን፣ የኦሮሞ ትምህርት ቢሮ በኦሮሚያ ውስጥ ያሉ አማሮችና ሌሎችም በቋንቋቸው መማር መብታቸው ነው ብለው ነው የደነገገሩት፡፡ ምክንያቱም የቋንቋ ጭቆና ምን እንደሆነ ስለምናውቀው በሌላ ጭቆና ማድረግ አንፈልግም፡፡›› ኦነግንም፣ ኦህዴድንም በዓላማ አስተሳስሮ ‹‹የኦነግ የፖለቲካ አላማ እና የአሁኑ የክልላዊ ህገ መንግስት ስታየው በኦሮሚያ ያሉ ዜጎች በሙሉ ኦሮሚያዊ ናቸው ነው የሚለው፡፡›› በሚል አንድም፣ ሁለትም፣ ሶስትም ነን ባይ ነው፡፡

‹‹ኢትዮጵያዊነት የተጫነብን ብልኮ ነው›› የሚለው ጃዋር ሌሎችን ‹‹ስትፈልግ ኢትዮጵያዊ ነኝ በል! ስትፈልግ አማራ ነኝ በል! ስትፈልግ ጎንደሬ ነኝ በል! ስትፈልግ የፈለገህን በል! በእኔ ላይ ግን የአንተን ማንነት ለመጫን አትሞክር….›› ብሎ በኃይለ ቃል ያስጠነቅቃል፡፡ በእርግጥም ምንም ሆነ ምን የእኔን ማንነት አሊያም እኔ የፈረጅኩትን ማንነት ተቀበል ማለት አግባብ አይደለም፡፡ ግን ጃዋር እንዲህ አስጠንቅቆ ሳይጨርስ እሱም ሌሎች ላይ የማፈልጉትን ብልኮ ይደርባል፣ እነሱ ነኝ በማይሉት ማንነት ይፈርጃቸዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ በቀዳሚነት የሚነሱት ስለ አገር አንድነት የሚያነሱትን ወገኖች ‹‹አማራ›› የሚል ብልኮ የሚጭንባቸው መሆኑ ነው፡፡ በስልክ ደውሎ ከአነጋገራቸው በኋላ አቋሙን እንዳስቀየሩት የሚናገርላቸው ‹‹የአማራ ልሂቃንም›› እንዲህ ብልኮ የተደረበባቸው ናቸው፡፡ ስለ አንድነት ያነሳ እሱ ባያምንበትም በጃዋር መመዘኛ ግን ‹‹አማራ›› ነው፡፡

ጃዋር በአንድ በኩል ‹‹አማራ›› የሚላቸው ልሂቃን የያዙት አቋም የሰፊው የአማራ ህዝብ አቋም አይደለም ይላል፡፡ ተመልሶ ደግሞ ‹‹ኦሮሚያ ውስጥ ያደጉት የነፍጠኛ ልጆች የአማራው ህዝብ የተሳሳተ አመለካከት እንዲይዝ አድርገውታል፡፡ ኦሮሞ ገና ቃሉ ሲነሳ አገር አፍራሽ፣ ጠበኛ የሚል አመለካከት በህዝቡ ውስጥ እንዲመጣ አደርገዋል፡፡ ከአሁን በፊት የነበሩት የአማራ ገዥዎችም ህዝቡ የተሳሳተ አመለካከት እንዲይዝ አድርገውታል፡፡›› በማለት የ‹‹አማራ ህዝብ የአማራ ልሂቃንን አስተሳሰብ እንደያዘ›› በገደምዳሜው ይከሳል፡፡ መጀመሪያ ላይ ‹‹የአማራ ልሂቃን አስተሳሰብ የሰፊው የአማራ ህዝብ አስተሳሰብ አይደለም፡፡›› ያለውን ወርድ ብሎ ‹‹ህዝቡን የተሳሳተ አመለካከት እንዲይዝ እድርገውታል›› ይለናል፡፡

ጃዋር ለወቅቱ አቋሙ ምክንያት አድርጎ የሚወስደው አንድም ደውሎ ያናገራቸው የ‹‹አማራ›› ልሂቃን አስተሳሰብ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ግብጽ ውስጥ ‹‹ኢትዮጵያዊ አይደለንም›› ብለው ግን ‹‹በቀኝ ዘመሙ›› የፖለቲካ ኃይል (ሚዲያ) ዘመቻ ተከፍቶባቸዋል በሚሉት ኦሮምኛ ወጣቶች ምክንያት ነው፡፡ በመሆኑም ይህ ጥቃት ቀዳሚ ትኩረት ማግኘት እንዳለበትና የአማራ ልሂቃን አስተሳሰብ አከርካሪውን መመታት እንዳለበት በመግለጽ ይህን የፖለቲካ ቡድን ቀዳሚ ጠላት አድርጎ ያቀርበዋል፡፡ ወደኋላ ላይ ደግሞ ጋዜጠኛ በፈቃዱ ሞረዳ ‹‹የኦሮሞ ህዝብ ጠላት ማን ነው?›› የሚል ጥያቄ ሲያቀርብለት ‹‹የኦሮሞ ህዝብ በራሱ ላይ ነው ማተኮር ያለበት›› በሚል ጠላት የሚባል ነገር ላይ ትኩረት እንደማያደርግ ይገልጻል፡፡ ግን ፖለቲካው ጃዋሪዝም ነውና አሁንም ማምታታቱን ይቀጥላል፡፡ በዚህ ወቅትም ህወሓት ቀዳሚው ጠላት ይሆናል፡፡ ቀደም ሲል ያላቸውን ጣል እርግፍ አድርጎም ‹‹አሁን ባለው ሁኔታ ‹‹አክቲቭ ኢነሚ›› ብለን የምንጠራው ህወሓትን ነው፡፡ ምንም ምንም ጭቅጭቅ የለውም፡፡›› እያለ ይቀጥላል፡፡ በደቂቃዎች ውስጥ የኦሮሞ ህዝብ ሶስትና ከዛ በላይ ጠላቶችና ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡት ግቦች ይቀመጡለታል፡፡ ‹‹የአንድነት ኃይሉን (አማራ ይለዋል) አከርካሪውን ከመምታት፣ በራሱ ላይ ትኩረት ማድረግ፣ ስርዓቱ (ህወሓት!) ላይ ‹‹ፎከስ›› ማድረግ….. ››

አብሮ ስለመስራትም ጃዋሪዝም ያው ማምታታት ነው፡፡ መጀመሪያ ላይ በደወለላቸው የ‹‹አማራ›› ልሂቃን መሰረት የኦሮሞ ህዝብ ራሱን ችሎ መስራት አለበት የሚል መደምደሚያ እንደደረሰ የሚናገረው ጃዋር ‹‹የእኛ እርሻ ላይ ዝናብ እየዘነበ ማንም ጋ አንሄድም፡፡›› ይላል፡፡ ትንሽ ቆይቶም ‹‹አብሮ ለመስራት መቼም ቢሆን ክፍት ነን፡፡›› በማለት ይህ ባህል ከድሮ የመጣ መሆኑን ያስረግጣል፡፡ ደግሞም እንደገና ‹‹ከሜጫና ቱለማ፣ እስከ መኢሶን፣ እስከ ኦነግ መሪዎች ለሁሉም የሚሆን መካከለኛ መንገድ ለመፍጠር ስርተዋል፣ መስዋትነትም ከፍለዋል፣ ያ መስዋትነታቸው ግን ሰሚ አላገኘም፡፡ እንዲናቁ ነው መንገድ የከፈተው፡፡›› በሚል ወደ መካከለኛ መንገድ ለመምጣት የሚደረገው ፖለቲካ መስዋዕትነት የሚያስከፍልና የማያወጣ አይነት እንደሆነ በገደምዳሜው ይገልጻል፡፡ አብረን መስራት አለብን፡፡ ዝግ አይደለንም እንዳላለ ‹‹እኛ ስንጎዳ ያ ጉዳት ዳግመኛ እንዳይደገም እርምጃ መውሰድ ያለብን እኛ ብቻ ነን፡፡›› በሚል ‹‹ብቻችን እንወጣዋለን!›› የሚል አቋሙን እንደገና ሊያጠናክር ይሞክራል፡፡

የ‹‹ብሄር/የእኛ እና እንሱ›› ፖለቲካ ስስ የሆነውን ጉዳይ በማጋጋል እውቅናን ማግኘት፣ ጥላቻ በመስበክ ደጋፊ ማሰባሰብ፣ ማምታታት ነው፡፡ ‹‹የእኛ እና እነሱ ፖለቲካ›› አመክኖ ሳይሆን የማነጻጸር አባዜ የተጠናወተው የማምታታት ፖለቲካ ነው፡፡ ይህ መነጻጸር የማይገባውን ነገር የማነጻጸር አባዜ የጃዋሪዝም ዋነኛ መገለጫ ነው፡፡

ምክንያታዊ ለሚባል ሰው፤ ሰው ምንም ይሁን ምን በህገ ወጥነት መታሰር የለበትም፡፡ አማርኛ ተናገረ፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ ተናገረ፣ሶማልኛ አሊያም ሌላ ቋንቋ በህገ ወጥ መንገድ መታሰር የለበትም፡፡ የግድ ሶስት ወይንም አራት ኦሮምኛ ተናጋሪ በህገ ወጥ መንገድ ከታሰረ ይህን ህገ ወጥነት መቃወም እየተቻለ፤ አምስት ወይንም ስድስት አማርኛ ወይንም ትግርኛ አሊያም ሌላ ቋንቋ ተናጋሪ ዜጋ መታሰር ነበረበት የሚል የስካር፣ ‹‹ጠባብ ብሄርተኝነት›› ያወረው ክርክር ሊቀርብ አይገባም፡፡
ለጃዋሪዝም ግን ይህ ሰብአዊም ሆነ ህጋዊ አመክኖ አይሰራም፡፡ ጃዋር ‹‹ዛሬ እስር ቤት ብትገባ ምርጥ የኦሮሞ ልጆችን እስር ቤት ውስጥ ነው የምታገኛቸው፡፡ አንድ የአማራ እስረኛ ካለ 90 የኦሮሞ እስረኛ አለ፡፡›› በሚል በኦሮምኛ ተናጋሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ‹‹አልተበደለም!›› ከሚለው ‹‹አማራ›› ጋር በማነጻጸር ‹‹ለመከራከር›› ይጥራል፡፡ እንደ ጃዋር የበርካታ ኦሮምኛ ተናጋሪዎች መታሰር ምክንያታዊ ሊሆን የሚችለው ሌሎች በህገ ወጥ መንገድም ቢሆን ከታሰሩ ብቻ ነው፡፡ ይህ አስተሳሰብ ልክ ርካሽ መጠጥ እንደሚያመጣው ‹‹ጠባብ ብሄርተኝነት›› የሚያመጣው ጭፍንና የማምታታት ፖለቲካ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ‹‹ማስተር ፕላን›› ለ‹‹ኦሮሞ ህዝብ ቆመናል›› የሚሉት አካላት አመክናዊ እንዳልሆኑ ካሳዩናቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ ነው፡፡ ‹‹ፊንፊኔ የኦሮሚያ ናት›› ይሉ እንዳልነበር በሌላ በኩል ደግሞ ‹‹አዲስ አበባ የኦሮሚያን መሬት እየወሰደች ነው፡፡›› የሚል የጃዋሪዝም ፖለቲካ ውስጥ ገቡ፡፡ በሂደት ስርዓቱ ‹‹ማስተር ፕላኑን›› የተቃወሙ ወጣቶችን በጠራራ ፀኃይ ጨፈጨፋቸው፡፡ በወቅቱ በተፈጠረው ችግር ሌላ ቋንቋ ተናጋሪዎችም ‹‹ከኦሮሚያ ውጡ ተብለው ተደብድበዋል፣ ተገድለዋል፡፡›› በተለይ ስለ ኢትዮጵያ አንድነት የሚያቀነቅኑ የፖለቲካ አካላት ጉዳዩን በግልጽ ለመደገፍ አልቻሉም፡፡ ምን ያህል ሰርተውበታል የሚለው እንዳለ ሆኖ ግድያውን ተቃውመው ሰልማዊ ሰልፍ ወጥተዋል፣ ሻማ አብርተው ጭፍጨፋውን ተቃውመዋል፣ መግለጫ አውጥተዋል፡፡ ይህም ቢሆን በቂ ላይሆን ይችላል፡፡ ጃዋር ተቃዋሚዎች ያደረጉትን ትንሽም ነገር ቢሆን በቂ አይደለም ከማለት ይልቅ ማብጠልጠሉን ነው የመረጠው፡፡

በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ትንሽም ቢሆን የሰሩትን ተቃዋሚዎች እያብጠለጠለ ለህወሓት መሳሪያ ሆኖ ተማሪዎቹን ያስጨፈጨፈውን ኦህዴድን በ‹‹ማስተር ፕላኑ›› ዙሪያ ለህወሓት ፈተና፣ በ‹‹ፊንፊኔ›› ጉዳይ ከህዝብ አሊያም ለ‹‹ኦሮሚያ›› ከቆሙ ሌሎች ኃይሎች ጋር ተመሳሳይ አቋም እንዳለው፣ ትግሉንም በማቀጣጠል ለወጣቱ አርዕያ አድርጎ ማወደሱ ነው፡፡ ግድያውን የተቃወሙት ተቃዋሚዎች በጃዋር የተብጠለጠሉት ግን በተማሪዎቹ ላይ የተፈጸመውን ግድያ በሚገባ አልተቃወሙም በሚል አይደለም፡፡ ጃዋር አሁንም ያነሳው ለመከራከሪያነት የማይበቃ ‹‹የጠባብ ብሄርተኝነት›› ማነጻጸሪያ ነው፡፡ ጃዋር የፖለቲካ ቡድኖቹ ለኦሮምኛ ተናጋሪ ተማሪዎች ላይ የተደረገውን ግድያ አልተቃወሙም ለማለት ያነሳው የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንን ነው፡፡ በኦሮሚያ ተማሪዎች በተፈጸመው ግድያ በቂ ምላሽ አልተሰጠም ብሎ ለመከራከር የዞን ዘጠኞች ላይ የተፈጸመው ህገ ወጥ እስር ተቃዋሚዎች ያሰሙት ተቃውሞ ተጋንኗል በሚል በመከራከሪያነት አቅርቦታል፡፡ ይህ ጃዋሪዝም ነው፡፡ የማይነጻጸረውን ማነጻጸር፣ በቅጽበት የተቃወሙትን መደገፍ፣ የደገፉትን መቃወም፣ አመክኖ ሲጠፋ ማምታታት!

Source – ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia

የጎዛምን ወረዳ የሰማያዊ አመራሮች በገዥው ፓርቲ አፈና እየተደረገባቸው መሆኑን አስታወቁ

$
0
0

• ‹‹ወጣትና አርሶ አደሩ ‹‹ለምን ከሰማያዊ አባላት ጋር ታወራላችሁ እየተባለ ይታሰራል››

በምስራቅ ጎጃም ጎዛምን ወረዳ በአባሊባኖስ ቀበሌ የሰማያዊ ፓርቲ ቅርንጫፍ አመራሮችና አባላት፣ ‹‹ለምን የሰማያዊ ፓርቲ አባል ሆናችሁ?›› በሚል ከፍተኛ አፈና እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
የወረዳው የፓርቲው አመራር የሆኑት አቶ አክሊሉ ውቤ፣ ወጣት ምህረት እንየውና አቶ አንመው ይዘንጋው ለነገረ ኢትዮጵያ እንደገለጹት የወረዳና የቀበሌ ባለስልጣናት የሰማያዊ አመራሮችን ከሰማያዊ ፓርቲ እንዲወጡ እንደሚያስገድዷቸው ገልጸዋል፡፡
blue party
አቶ አንመው ይዘዘው የተባለውን የፓርቲው አባል መስከረም 14/2007 ዓ.ም ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ ሚሊሻ ጥሩነህ መኮንን፣ ሚልሻ ሽታሁን ዘውዴ፣ ሚሊሻ አበባየሁ አባተ አስገድደው ወደ ቀበሌው ቢሮ በመውሰድ የቀበሌው ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በልስቲ ትዛዜ ከሰማያዊ ፓርቲ ካልወጣ እንደሚገረፍ፣ ካልሆነ አገር ጥሎ መሰደድ እንዳለበት እንደዛቱበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

የቀበሌው ሊቀመንበር ‹‹ኢህአዴግ በ1997 ምርጫ ቢሸነፍም ሰራዊቱም፣ ወታደሩም፣ ፖሊሱም፣ የኛ ነው፣ እናንተ ወረቀትና እስክርቢቶ ይዛችሁ ልታሸንፉ አትችሉም፤ አሁንም እርምጃ እንወስድባችኋለን›› በሚል እንደዛቱበትና ከፓርቲው እንዲወጣ እንዳስጠነቀቁት ገልጾአል፡፡

በተመሳሳይ አቶ አክሊሉ ውቤ የተባሉትን ግለሰብ ‹‹ቢያርፍ ይረፍ ከፖለቲካ ድርጅት መውጣት አለበት፣ ካላረፈ ለህይወቱ ያሰጋዋል›› በሚል የቀበሌው ሹም የሆኑት አቶ ገነነ እና አቶ በልስቲ ትዕዛዜ እንደዛቱባቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ምህረቱ ይታየው የተባለው ወጣትም ተመሳሳይ ማስፈራሪያ እንደደረሰበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

በሌላ በኩል አቶ በልስቲ ትዕዛዜ፣ ኮማንደር አንተነህ ፈንታሁን፣ አቶ ተሻገር አዲሱ የተባሉት የቀበሌው ባለስልጣናት ‹‹ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ለምን ታወራላችሁ፣ ለምን ከእነሱ ጋር ትቆማላችሁ›› በሚል በየዕለቱ ወጣቱንና አርሶ አደሩን እንደሚያስሩ የወረዳው የፓርቲው ቅርንጫፍ አመራሮች ለነገረ ኢትዮጵያ አክለው ገልጸዋል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ገዥው ፓርቲ ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ በከፈተባቸው ቦታዎች ቢሮዎችን ለመዝጋት፣ ቢሮ ለመክፈት እየጣረ በሚገኝባቸው ቦታዎች ደግሞ አባላቱንና አመራሮቹ ከፓርቲው እንዲወጡ ጫና እያደረገ እንደሚገኝ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ጃዋሪዝም (የማምታታት ፖለቲካ) –በጌታቸው ሽፈራው (የግል አስተያየት)

$
0
0

‹‹(ጠባብ) ብሄርተኝነት ልክ እንደ ርካሽ መጠጥ ነው፡፡ መጀመሪያ እንድትጠጣው ይገፋህና ያሰክርሃል፡፡ ቀጥሎ አይንህን ያውርሃል፡፡ ከዛም ይገድልሃል፡፡›› ዳን ፍሪድ

በጌታቸው ሺፈራው
(የግል አስተያየት)

ጃዋር መሃመድ ከአመታት በፊት ከማደንቃቸው ኢትዮጵያዊ አክቲቪስቶች መካከል አንዱ ነበር፡፡ በተለይ ይህ ወጣት ከጥቂት አመታት በፊት እነ በረከት ስምኦንን አልጀዚራ ላይ ሲያፋጥጣቸው ሳይ አድናቆቴ ከፍ ብሎ ነበር፡፡ በዚህ ወቅት ጃዋር ወደ ሶማሊያ ዘው ብሎ ስለገባው ሰራዊት፣ ቋንቋ ሳይለይ በየትኛውም ኢትዮጵያዊ ላይ የሚደርሰውን በደል ሽንጡን ገትሮ መከራከሩ ይታወሳል፡፡ ግን ምን ያደርጋል ይህ አቋሙ እንደተጠበቀው ሊዘልቅ አልቻለም፡፡ መሃል ላይ የ‹‹እኛ እና እነሱ›› ብልሹ ፖለቲካ ሰለባ ሆነ፡፡

በተለይ በአንድ ወቅት አልጀዚራ ላይ ቀርቦ ‹‹በቅድሚያ ኦሮሞ ነኝ›› ካለ በኋላ የፖለቲካ አቋሙ እየተንሸራተተ ሜንጫን እንደ ህጋዊ ነገር ማንሳት ውስጥ ገባ፡፡ አንዴ ‹‹ኢትዮጵያዊ ሙስሊም›› ሆኖ የኦሮሞ ሙስሊሞች ነጻነት ለሌላው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ነጻነትም ወሳኝ ነው ሲል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክርስቲያኑን ኦሮሞ በሜንጫ አንገቱን ስለመቅላት ይሰብካል፡፡ (ይህን መረጃ የተቀነባበረ ነው የሚል መረጃ ያቅርብ)፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ክርስቲያኑን ኦሮምኛ ተናጋሪም ጭምር ወክሎ ‹‹ቅድሙያ ኦሮሞ ነኝ›› አለ፡፡

ከዚህ ውጣ ውረድ በኋላ ጃዋር በቅርቡ ከ‹‹ኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ›› ጋር ቃለ መጠይቅ አድርጓል፡፡ በቃለ መጠይቁ እስካሁን አሉ የሚላቸውን ብዥታዎች ለማጥራትና አቋሞቹንም ለማስረገጥ በሚመስል መልኩ የቀረበ ይመስላል፡፡ በዚህ ቃለ መጠይቅ ጃዋር ከዛ በፊት እንዳደረጋቸው አነጋጋሪ ነገሮች ባይኖሩትም ቃለ መጠይቁ በሙሉ ‹‹ምክንያታዊ ናቸው›› በሚላቸው ምክንያት አልባ የማምታታት ክርክሮች የተሞሉ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ፡፡

በቃለ መጠይቁ አልጀዚራ ላይ ‹‹መጀመሪያ ኦሮሞ ነኝ›› ያለበትን አቋሙን የሚያጠናክርበት ነው፡፡ ‹‹በልጅነቴ ነው በፖለቲካው ተጠምቄ ያደኩት›› የሚለው ጃዋር ‹‹ከተወለድኩበት ጊዜ ጀምሮ እስከምሞትበት ጊዜ ድረስ ከምንም ከማን በላይ ራሴን እንደ ኦሮሞ ነው የማያው፡፡›› ሲል በ‹‹ማንነቱ›› ሁኔታ ላይ ይደመድማል፡፡ ግን በዚሁ ቃለ መጠይቅም ቢሆን ከአንድ አቋም ወደ ሌላ አቋም ሲዘል ታይቷል፡፡
jawar
ጋዜጠኛው ‹‹ኦሮሞ ፈርስት›› የሚለው ጉዳይ ከመነሳቱ በፊት ኢትዮጵያዊ በሆኑ አጀንዳዎች ይሳተፍ እንደነበር በመግለጽ ከዛ በኋላ አቋም መቀየር አለመቀየሩን ሲጠይቀው ‹‹አልቀየርኩም›› ይላል፡፡ መልሶ ደግሞ ‹‹አየህ! ከ2008፣ 2009 በኋላ ‹ኮንሸስ› የሆነ ምርጫ አድርጌያለሁ፡፡ በተለይ ከአማራ ልሂቃን ጋር በመገናኘት ለእነሱ ስለ ኦሮሞ ህዝብ ትግል በማስረዳት ከእነሱ ጋር አብሮ ለመስራት ይቻላል የሚል እምነት ነበረኝ፡፡ የአማራ ልሂቃን በኦሮሞ ትግል ላይ ያላቸው አመለካከት በጣም የሚያስደነግጥና በጣም የሚያስፈራ ነበር፡፡ በትምህርት ጥናቴም ሆነ ባለኝ ቀረቤት ችግሩ ምንድን ነው ብየ ሳስበው ምን አልባት ካለማወቅ (ኢግኖራስን) የመነጨ ነው የሚል ነበር፡፡ ሁለቱንም አካል ወደ መሃል በማምጣል አብሮ መስራት ይቻላል በሚል አምስት አመት ያህል ነው የሰራሁት፡፡ ነገር ግን ያለው ችግር የግዝብተኝነት (አሮጋንስ) ችግር እንዳለ ተረዳሁ፡፡ ኦሮሞ ፈርስት የሚለው ከመምጣቱ በፊት ስርቤይ አድርጌ ነበር፡፡ …27 ያህል ሰዎችን ደውየ 1 ወይም 2 ብቻ ናቸው የተቀበሉት፡፡ እንዲሁም የኦሮሞ ትግል እየተዳከመ በመጣ ቁጥር ያላቸው ንቀት እየተጠናረ ሄደ›› በሚል አቋሙን መቼ እንደቀየረ ለማስገንዘብ ሲጥር ‹‹ከተወለድኩ ጀምሮ እስከሞት ድረስ ኦሮሞ ነኝ›› የሚለው የ‹‹አሁኑ›› አቋሙንም ራሱ መልሶ ይከራከረዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ሌላ አቋሙን የቀየረበት ምክንያት እንዳለው ጃዋር እንዲህ ያስረዳል፡፡ ‹‹…በግብጽ የሚገኙ የኦሮሞ ስደተኞች በአባይ ጉዳይ ላይ ኢትዮጵያና ግብጽ ባለባቸው ችግር ጥቃት ሲደርስባቸው ‹‹እኛ ኦሮሞዎች ነን፡፡ ከኢትጵያ መንግስት ጋር ምንም ትስስር የለንም ሲሉ እንዴት አባታችሁ ኦሮሞዎች ነን ትላላችሁ የሚል በጣም አጸያፊ የሆነ የሚዲያ ዘመቻ ተጀመረባቸው፡፡ ያ ለእኔ ቀይ መስመሩን ያለፉበት እንደሆነና ……በዚህም በማንነታችን ላይ የተነጣጠረ ጥቃት ነው ወደሚል ገባሁ›› ይለናል፡፡ እንደ ጃዋር ከሆነ ግብጽ ውስጥ አማርኛ፣ ትግርኛ፣ ሲዳምኛ….. ተናጋሪዎች የሉም፡፡ አሊያም ጥቃት አልደረሰባቸውም፡፡ ወይንም ደግሞ ነገ ጃዋር ቆሜለታለሁ በሚለው ኦሮሞነታቸው ግብጾች ጥቃት የሚያደርሱባቸው ሲሆን ‹‹እኛ ኦሮሞዎች አይደለንም፣ ከኦሮሞ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የለንም፡፡›› ቢሉ ትክክል ናቸው እንደማለት ነው፡፡

በዚህ ቃለ መጠይቅ ጃዋር ተራ የሀሳብና የአመክኖ ማምታታት ብቻ አይደለም የሚታይበት፡፡ አንዴ መለስ ዜናዊ፣ ሌላ ጊዜ ኦነግ፣ አሊያም ኦህዴድ የያዙትን አቋም አቋሙ አድር ሲከራከርበት፣ ‹‹እኛ›› እያለ ሲገልጽ ተስተውሏል፡፡

ለአብነት ያህል 27 ያህል የ‹‹አማራ ልሂቃንን›› አነጋግሬ አገኘሁት የሚለውን መደምደሚያ ሲገልጽ ነፍጠናውን አከርካሪው ሰብረነዋል የሚለውን አቶ መለስ አቋም በግልጽ እንደተጋራ ይታያል፡፡ ጃዋር ‹‹ይህን አሮጋንስ ማስተካከል የሚቻለው … ቀኝ ዘመሙን የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት አከርካሪውን በመስበር እጅ ማሰጠት ነው፡፡ ያ ፖለቲካ እንደማይሰራ ወደ ‹ኮምፕሊት ፖለቲካል ባንክራፕሲ› ማስገባት ግዴታ ነው በሚለው መደምደሚያ ደርሼ ነበር፡፡›› ይላል፡፡ ይህኔ ጃዋር መለስን መለስን ነው የሚመስለው፡፡

ኦህዴድ ከገዥው ቡድን ጋር ተባብሮ የኦሮሞን ህዝብ እየበደለ ስለመሆኑ ለተነሳለት ጥያቄ ጃዋር ኦህዴድን ምንም አቅም የሌለው አድርጎ ይገልጸዋል፡፡ መልሶ ደግሞ ለህወሓት ፈታኙ ኦህዴድ ነው እያለ ያምታታል፡፡ ጃዋር መጀመሪያ ‹‹ለእኔ የኦህዴድ አመራሮችም ሆነ አባላት በአንድ ፋብሪካ የሚሰሩ የፋብሪካ ዩኒየን ያህል ጉልበት የሌላቸውና የማይፈቀድላቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ከተፈጠረበት ጊዜ ድረስ እስካሁን ድረስ ምንም አይነት ድርጅታዊ ስብዕና የሌለው ድርጅት ነው፡፡›› በማለት ከምንም የማይገባ፣ ለምንም የማይሆን አቅመ ቢስ ያደርገዋል፡፡

ምንም አቅም የላቸውም ያለውን ተመልሶ ‹‹..ህወሓት እንደፈለገው ኦህዴድ ቡችላ የሚሆንለት አይደለም፡፡ ምክንያቱም ብዙ ያልነቁት በእድሜ እየገፉ በሄዱ ቁጥር፣ ከኦነግ ጋርም ለመሻማት የተማሩትን ወደ ድርጅቱ እየከተተ በሄደ ቁጥር፣ ኦህዴድ እንደ ድርጅት ባይጠናከርም ግለሰቦች በተቻለ መጠን የህዝቡን መብት ለማስጠበቅ እየተንቀሳቀሱ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ እንዲያውም በአሁኑ ወቅት ለህወሓት ከማንም በላይ አስፈሪው ኦህዴድ ሆኖ ያለበትና ባለፉት ሁለት አመታት የምናየው ዳይናሚክስ ከፍተኛ አደጋ እየፈጠሩበት እንዳለ ነው የምናየው፡፡›› በማለት በቅጽበት ኦህዴድን ከአነስተኛ ፋብሪካ ዩኒየንነት ወደ ግዙፍና አስፈሪ ፓርቲነት ያሳድገዋል፡፡

ጃዋር መጀመሪያ ‹‹እንደ ድርጅት አልቆጥረውም፤ አቅመ ቢስ ነው፡፡›› ስላለው ኦህዴድ ይቀጥላል፡፡ ‹‹ያ ብቻ አይደለም የተማሩ ኦሮሞዎችን በግዳጅ ወደ ቢሮክራሲው አስገብቷል፡፡ እነዚህ ግለሰቦች ቢያንስ ከስርዓቱ ጋር እምብይ ማለት ቢያቅታቸው ‹አክቲቭሊ› ህዝቡን መበደል እያደረሱ አይደለም፡፡ …..ከዚህም የተነሳ በኦነግ የተጀመሩ ብዙ ፕሮጀክቶችን ወደማጠናቀቀ እየደረሱ ነው ያለው›› በማለት ኦህዴድን የኦነግ ‹‹ራዕይ አስቀጣይ›› ያደርገዋል፡፡ ይፈጽማል ከሚባለው ኃጥያት ነጻ ሊያወጣው ይሞክራል፡፡

ጃዋር ከአንድ የፋብሪካ ማህበር አይሻሉም የሚላቸውን ኦህዴዶች እንደገና ሲያማካሻቸው ጋዜጠኛው ‹‹ስለዚህ የኦህዴድ መኖር አስፈላጊ ነው?›› ብሎ ይጠይቃል፡፡ ጃዋር ግን አሁንም ያምታታል፡፡ ‹‹አይደለም!›› ይላል፡፡ ግን ደግሞ ስለ ኦህዴድ አስፈላጊነት እንዲህ ይገልጻል፡፡ ‹‹በአሁኑ ወቅት ወደ 90 በመቶ የሚሆነው የኦሮሞ ልሂቃን ኦህዴድ ውስጥ ነው ያለው፡፡ ስለዚህ ቀጣዩ የኦሮሚያ እጣ ፈንታ በእነሱ እጅ ነው ያለው፡፡›› በማለት መኖሩ አስለላጊ አይደለም የተባለው ኦህዴድ የኦሮሚያ እጣ ፈንታ ሆኖት ያርፋል፡፡ ጃዋሪዝም እንዲህ በደቂቃዎች አቋምን የመቀየር፣ የመቀያየር፣ የማምታታት ፖለቲካ ነው!

jawarይህ እንግዲህ ጃዋር ነው፣ ፖለቲካው ደግሞ ጃዋሪዝም፡፡ ስለዚህ አሁንም ማምታታቱን ይቀጥላል፡፡ እናም በአዲስ አበባ ‹‹መሪ እቅድ ወይም ማስተር ፕላን›› ላይ ለተነሳው ተቃውሞ ኦህዴዶች አሉበት እንደሚባል ጋዜጠኛው ሲያስታውሰው ‹‹ማንኛውም ኦሮሞ ኦህዴድም ሆነ ኦነግ ‹‹ማንነት፣ ኦሮሞ የሚባል ነገርና አዲስ አበባ ጉዳይ አንድ ናቸው›› በማለት ኦህዴድን ከማህበር ወደ ለህዝብ እንደሚያስብና አላማ ያለው የፖለቲካ ድርጅት ያደርገዋል፡፡ በአብዛኛው የቃለ መጠይቅ ክፍል መጀመሪያ ላይ ‹‹የዩኒየን አቅም ያህል የሌላቸው›› ያላቸውን ኦህዴዶች ያሞገሰበት ነው፡፡ ‹‹የዛሬ 9 አመት አካባቢ ዋና ከተማው ወደ አዳማ ሲዛወር ኦህዴድ ከፍተኛ ተቃውሞ ማድረጉን፤ ወደ ዋና ከተማውን አዲስ አበባ ማስመለሳቸውን በመግለጽ ‹‹የዩኒየን ያህል አቅም የላቸውም፣ የፖለቲካ ድርጅትም አይደሉም ስላላቸው መወድስ ያቀርባል፡፡

አሁን በአዲስ አበባ በተፈጠረው ችግር ደግሞ ‹‹በኢህዴድ ውስጥ አንድም ልዩነት ሳይፈጠር በአመራሩ በአንድ አቋም የተቃወሙበት ነበር፡፡ በግልጽ የህወሓትን ሰዎች ተቃውመዋቸዋል፡፡ በህወሓትና በኦህዴድ ጉዳይ ላይ በዚህ ጉዳይ ላይ የነበረውን ልዩነት ከአሁን ቀደም ኖሮ አያውቅም፡፡ ከዚያ አልፎ ያን ተቃውሞ ህዝቡ እንዲያውቀው በቴሊቪዝን አስተላልፈዋል፡፡ ይህን በማድረጋቸው ብዙ ሰዎች ለስራቸውም፣ ለህይወታቸውም ለቤተሰቦቻቸውም ራሳቸውን አደጋ ላይ አጋልጠዋል፡፡ ወጣቱም እነሱን ተከትሎ ነው ወደ ትግል የገባው›› በሚል የትግሉ አንቀሳቃሽ ሞተሮች፣ ነጻ አውጭዎች ያደርጋቸዋል፡፡

‹‹በኦህዴድ ውስጥ እከሌን እናጥቃ እከሌን እንግደል ቢሉ የባሰ ችግር ውስጥ ስለሚገቡ እስካሁን እየተፋጠጡ፣ በተቻለ መጠን ኢህዴዶችን በሁለት ከፍለው እያጋጩ ለማዳከም ሙከራ እያደረጉ ነው ያሉት፡፡ ባለፈው ሳምንት ሁለት፤ ሶስት ስብሰባ ተደርጎ ኦህዴዶች በአንድ አቋም ነው ተስማምተው የወጡት፡፡ እናም (ህወሓቶች) የተሳካላቸው አይመስለኝም፡፡›› በማለት ከጠንካራው ኦህዴድ ጎን ሆኖ ህወሓት አቅመ ቢስ እንደሆነ ያወራል፡፡ መቸም መጀመሪያ ላይ ‹‹የዩኒየንን ያህል አቅም የለውም የተባለው ድርጅትና ይህኛው ኦህዴድ በአንድ ሰው፣ ደግሞም በአንድ ቃለ መጠይቅ ላይ፣ በሴኮንድና ደቂቃዎች ልዩነት የተነሳ መከራከሪያ ነው ብሎ ለማመን ይከብዳል፡፡ ግን የሆነው ይህ ነው፡፡ ምክንያቱም ፖለቲካው ማምታታት ነው፡፡ ጃዋሪዝም!

ጃዋር መጀመሪያ ላይ ‹‹አሽከር›› አድርጎ የሚያቀርባቸው ኦህዴዶች ወደ መጨረሻ አናብስት ይሆናሉ፡፡ እነዚህን ‹‹አናብስቶች›› የእራሱ አድርጎ ስለሚቆጥራቸው ኦህዴድን ሰራው የሚለውን ሁሉ ‹‹እኛ እንዲህ አድርገን›› እያለ ይገልጸዋል፡፡ ኦህዴድን እቃወማለሁ እያለ ኦህዴድ ሆኖ (እኛ እያለ) ኦህዴድ ስኬቴ ስለሚለው ‹‹ስኬት›› ይናገራል፡፡ ኦህዴድ አሰራኋቸው የሚላቸውን መሰረተ ልማቶች ‹‹የእኛ›› ሲል አፍለኛ የኦህዴድ ካድሬ ይመስላል፡፡ እንዲህ! ‹‹በተጨባጭ ያሳየነውም ይህንኑ ነው፡፡…….ህወሓት እምብይ እያለ የኦሮሞ ልሂቃን፣ የኦሮሞ ትምህርት ቢሮ በኦሮሚያ ውስጥ ያሉ አማሮችና ሌሎችም በቋንቋቸው መማር መብታቸው ነው ብለው ነው የደነገገሩት፡፡ ምክንያቱም የቋንቋ ጭቆና ምን እንደሆነ ስለምናውቀው በሌላ ጭቆና ማድረግ አንፈልግም፡፡›› ኦነግንም፣ ኦህዴድንም በዓላማ አስተሳስሮ ‹‹የኦነግ የፖለቲካ አላማ እና የአሁኑ የክልላዊ ህገ መንግስት ስታየው በኦሮሚያ ያሉ ዜጎች በሙሉ ኦሮሚያዊ ናቸው ነው የሚለው፡፡›› በሚል አንድም፣ ሁለትም፣ ሶስትም ነን ባይ ነው፡፡

‹‹ኢትዮጵያዊነት የተጫነብን ብልኮ ነው›› የሚለው ጃዋር ሌሎችን ‹‹ስትፈልግ ኢትዮጵያዊ ነኝ በል! ስትፈልግ አማራ ነኝ በል! ስትፈልግ ጎንደሬ ነኝ በል! ስትፈልግ የፈለገህን በል! በእኔ ላይ ግን የአንተን ማንነት ለመጫን አትሞክር….›› ብሎ በኃይለ ቃል ያስጠነቅቃል፡፡ በእርግጥም ምንም ሆነ ምን የእኔን ማንነት አሊያም እኔ የፈረጅኩትን ማንነት ተቀበል ማለት አግባብ አይደለም፡፡ ግን ጃዋር እንዲህ አስጠንቅቆ ሳይጨርስ እሱም ሌሎች ላይ የማፈልጉትን ብልኮ ይደርባል፣ እነሱ ነኝ በማይሉት ማንነት ይፈርጃቸዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ በቀዳሚነት የሚነሱት ስለ አገር አንድነት የሚያነሱትን ወገኖች ‹‹አማራ›› የሚል ብልኮ የሚጭንባቸው መሆኑ ነው፡፡ በስልክ ደውሎ ከአነጋገራቸው በኋላ አቋሙን እንዳስቀየሩት የሚናገርላቸው ‹‹የአማራ ልሂቃንም›› እንዲህ ብልኮ የተደረበባቸው ናቸው፡፡ ስለ አንድነት ያነሳ እሱ ባያምንበትም በጃዋር መመዘኛ ግን ‹‹አማራ›› ነው፡፡

ጃዋር በአንድ በኩል ‹‹አማራ›› የሚላቸው ልሂቃን የያዙት አቋም የሰፊው የአማራ ህዝብ አቋም አይደለም ይላል፡፡ ተመልሶ ደግሞ ‹‹ኦሮሚያ ውስጥ ያደጉት የነፍጠኛ ልጆች የአማራው ህዝብ የተሳሳተ አመለካከት እንዲይዝ አድርገውታል፡፡ ኦሮሞ ገና ቃሉ ሲነሳ አገር አፍራሽ፣ ጠበኛ የሚል አመለካከት በህዝቡ ውስጥ እንዲመጣ አደርገዋል፡፡ ከአሁን በፊት የነበሩት የአማራ ገዥዎችም ህዝቡ የተሳሳተ አመለካከት እንዲይዝ አድርገውታል፡፡›› በማለት የ‹‹አማራ ህዝብ የአማራ ልሂቃንን አስተሳሰብ እንደያዘ›› በገደምዳሜው ይከሳል፡፡ መጀመሪያ ላይ ‹‹የአማራ ልሂቃን አስተሳሰብ የሰፊው የአማራ ህዝብ አስተሳሰብ አይደለም፡፡›› ያለውን ወርድ ብሎ ‹‹ህዝቡን የተሳሳተ አመለካከት እንዲይዝ እድርገውታል›› ይለናል፡፡

ጃዋር ለወቅቱ አቋሙ ምክንያት አድርጎ የሚወስደው አንድም ደውሎ ያናገራቸው የ‹‹አማራ›› ልሂቃን አስተሳሰብ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ግብጽ ውስጥ ‹‹ኢትዮጵያዊ አይደለንም›› ብለው ግን ‹‹በቀኝ ዘመሙ›› የፖለቲካ ኃይል (ሚዲያ) ዘመቻ ተከፍቶባቸዋል በሚሉት ኦሮምኛ ወጣቶች ምክንያት ነው፡፡ በመሆኑም ይህ ጥቃት ቀዳሚ ትኩረት ማግኘት እንዳለበትና የአማራ ልሂቃን አስተሳሰብ አከርካሪውን መመታት እንዳለበት በመግለጽ ይህን የፖለቲካ ቡድን ቀዳሚ ጠላት አድርጎ ያቀርበዋል፡፡ ወደኋላ ላይ ደግሞ ጋዜጠኛ በፈቃዱ ሞረዳ ‹‹የኦሮሞ ህዝብ ጠላት ማን ነው?›› የሚል ጥያቄ ሲያቀርብለት ‹‹የኦሮሞ ህዝብ በራሱ ላይ ነው ማተኮር ያለበት›› በሚል ጠላት የሚባል ነገር ላይ ትኩረት እንደማያደርግ ይገልጻል፡፡ ግን ፖለቲካው ጃዋሪዝም ነውና አሁንም ማምታታቱን ይቀጥላል፡፡ በዚህ ወቅትም ህወሓት ቀዳሚው ጠላት ይሆናል፡፡ ቀደም ሲል ያላቸውን ጣል እርግፍ አድርጎም ‹‹አሁን ባለው ሁኔታ ‹‹አክቲቭ ኢነሚ›› ብለን የምንጠራው ህወሓትን ነው፡፡ ምንም ምንም ጭቅጭቅ የለውም፡፡›› እያለ ይቀጥላል፡፡ በደቂቃዎች ውስጥ የኦሮሞ ህዝብ ሶስትና ከዛ በላይ ጠላቶችና ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡት ግቦች ይቀመጡለታል፡፡ ‹‹የአንድነት ኃይሉን (አማራ ይለዋል) አከርካሪውን ከመምታት፣ በራሱ ላይ ትኩረት ማድረግ፣ ስርዓቱ (ህወሓት!) ላይ ‹‹ፎከስ›› ማድረግ….. ››

አብሮ ስለመስራትም ጃዋሪዝም ያው ማምታታት ነው፡፡ መጀመሪያ ላይ በደወለላቸው የ‹‹አማራ›› ልሂቃን መሰረት የኦሮሞ ህዝብ ራሱን ችሎ መስራት አለበት የሚል መደምደሚያ እንደደረሰ የሚናገረው ጃዋር ‹‹የእኛ እርሻ ላይ ዝናብ እየዘነበ ማንም ጋ አንሄድም፡፡›› ይላል፡፡ ትንሽ ቆይቶም ‹‹አብሮ ለመስራት መቼም ቢሆን ክፍት ነን፡፡›› በማለት ይህ ባህል ከድሮ የመጣ መሆኑን ያስረግጣል፡፡ ደግሞም እንደገና ‹‹ከሜጫና ቱለማ፣ እስከ መኢሶን፣ እስከ ኦነግ መሪዎች ለሁሉም የሚሆን መካከለኛ መንገድ ለመፍጠር ስርተዋል፣ መስዋትነትም ከፍለዋል፣ ያ መስዋትነታቸው ግን ሰሚ አላገኘም፡፡ እንዲናቁ ነው መንገድ የከፈተው፡፡›› በሚል ወደ መካከለኛ መንገድ ለመምጣት የሚደረገው ፖለቲካ መስዋዕትነት የሚያስከፍልና የማያወጣ አይነት እንደሆነ በገደምዳሜው ይገልጻል፡፡ አብረን መስራት አለብን፡፡ ዝግ አይደለንም እንዳላለ ‹‹እኛ ስንጎዳ ያ ጉዳት ዳግመኛ እንዳይደገም እርምጃ መውሰድ ያለብን እኛ ብቻ ነን፡፡›› በሚል ‹‹ብቻችን እንወጣዋለን!›› የሚል አቋሙን እንደገና ሊያጠናክር ይሞክራል፡፡

የ‹‹ብሄር/የእኛ እና እንሱ›› ፖለቲካ ስስ የሆነውን ጉዳይ በማጋጋል እውቅናን ማግኘት፣ ጥላቻ በመስበክ ደጋፊ ማሰባሰብ፣ ማምታታት ነው፡፡ ‹‹የእኛ እና እነሱ ፖለቲካ›› አመክኖ ሳይሆን የማነጻጸር አባዜ የተጠናወተው የማምታታት ፖለቲካ ነው፡፡ ይህ መነጻጸር የማይገባውን ነገር የማነጻጸር አባዜ የጃዋሪዝም ዋነኛ መገለጫ ነው፡፡

ምክንያታዊ ለሚባል ሰው፤ ሰው ምንም ይሁን ምን በህገ ወጥነት መታሰር የለበትም፡፡ አማርኛ ተናገረ፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ ተናገረ፣ሶማልኛ አሊያም ሌላ ቋንቋ በህገ ወጥ መንገድ መታሰር የለበትም፡፡ የግድ ሶስት ወይንም አራት ኦሮምኛ ተናጋሪ በህገ ወጥ መንገድ ከታሰረ ይህን ህገ ወጥነት መቃወም እየተቻለ፤ አምስት ወይንም ስድስት አማርኛ ወይንም ትግርኛ አሊያም ሌላ ቋንቋ ተናጋሪ ዜጋ መታሰር ነበረበት የሚል የስካር፣ ‹‹ጠባብ ብሄርተኝነት›› ያወረው ክርክር ሊቀርብ አይገባም፡፡
ለጃዋሪዝም ግን ይህ ሰብአዊም ሆነ ህጋዊ አመክኖ አይሰራም፡፡ ጃዋር ‹‹ዛሬ እስር ቤት ብትገባ ምርጥ የኦሮሞ ልጆችን እስር ቤት ውስጥ ነው የምታገኛቸው፡፡ አንድ የአማራ እስረኛ ካለ 90 የኦሮሞ እስረኛ አለ፡፡›› በሚል በኦሮምኛ ተናጋሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ‹‹አልተበደለም!›› ከሚለው ‹‹አማራ›› ጋር በማነጻጸር ‹‹ለመከራከር›› ይጥራል፡፡ እንደ ጃዋር የበርካታ ኦሮምኛ ተናጋሪዎች መታሰር ምክንያታዊ ሊሆን የሚችለው ሌሎች በህገ ወጥ መንገድም ቢሆን ከታሰሩ ብቻ ነው፡፡ ይህ አስተሳሰብ ልክ ርካሽ መጠጥ እንደሚያመጣው ‹‹ጠባብ ብሄርተኝነት›› የሚያመጣው ጭፍንና የማምታታት ፖለቲካ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ‹‹ማስተር ፕላን›› ለ‹‹ኦሮሞ ህዝብ ቆመናል›› የሚሉት አካላት አመክናዊ እንዳልሆኑ ካሳዩናቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ ነው፡፡ ‹‹ፊንፊኔ የኦሮሚያ ናት›› ይሉ እንዳልነበር በሌላ በኩል ደግሞ ‹‹አዲስ አበባ የኦሮሚያን መሬት እየወሰደች ነው፡፡›› የሚል የጃዋሪዝም ፖለቲካ ውስጥ ገቡ፡፡ በሂደት ስርዓቱ ‹‹ማስተር ፕላኑን›› የተቃወሙ ወጣቶችን በጠራራ ፀኃይ ጨፈጨፋቸው፡፡ በወቅቱ በተፈጠረው ችግር ሌላ ቋንቋ ተናጋሪዎችም ‹‹ከኦሮሚያ ውጡ ተብለው ተደብድበዋል፣ ተገድለዋል፡፡›› በተለይ ስለ ኢትዮጵያ አንድነት የሚያቀነቅኑ የፖለቲካ አካላት ጉዳዩን በግልጽ ለመደገፍ አልቻሉም፡፡ ምን ያህል ሰርተውበታል የሚለው እንዳለ ሆኖ ግድያውን ተቃውመው ሰልማዊ ሰልፍ ወጥተዋል፣ ሻማ አብርተው ጭፍጨፋውን ተቃውመዋል፣ መግለጫ አውጥተዋል፡፡ ይህም ቢሆን በቂ ላይሆን ይችላል፡፡ ጃዋር ተቃዋሚዎች ያደረጉትን ትንሽም ነገር ቢሆን በቂ አይደለም ከማለት ይልቅ ማብጠልጠሉን ነው የመረጠው፡፡

በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ትንሽም ቢሆን የሰሩትን ተቃዋሚዎች እያብጠለጠለ ለህወሓት መሳሪያ ሆኖ ተማሪዎቹን ያስጨፈጨፈውን ኦህዴድን በ‹‹ማስተር ፕላኑ›› ዙሪያ ለህወሓት ፈተና፣ በ‹‹ፊንፊኔ›› ጉዳይ ከህዝብ አሊያም ለ‹‹ኦሮሚያ›› ከቆሙ ሌሎች ኃይሎች ጋር ተመሳሳይ አቋም እንዳለው፣ ትግሉንም በማቀጣጠል ለወጣቱ አርዕያ አድርጎ ማወደሱ ነው፡፡ ግድያውን የተቃወሙት ተቃዋሚዎች በጃዋር የተብጠለጠሉት ግን በተማሪዎቹ ላይ የተፈጸመውን ግድያ በሚገባ አልተቃወሙም በሚል አይደለም፡፡ ጃዋር አሁንም ያነሳው ለመከራከሪያነት የማይበቃ ‹‹የጠባብ ብሄርተኝነት›› ማነጻጸሪያ ነው፡፡ ጃዋር የፖለቲካ ቡድኖቹ ለኦሮምኛ ተናጋሪ ተማሪዎች ላይ የተደረገውን ግድያ አልተቃወሙም ለማለት ያነሳው የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንን ነው፡፡ በኦሮሚያ ተማሪዎች በተፈጸመው ግድያ በቂ ምላሽ አልተሰጠም ብሎ ለመከራከር የዞን ዘጠኞች ላይ የተፈጸመው ህገ ወጥ እስር ተቃዋሚዎች ያሰሙት ተቃውሞ ተጋንኗል በሚል በመከራከሪያነት አቅርቦታል፡፡ ይህ ጃዋሪዝም ነው፡፡ የማይነጻጸረውን ማነጻጸር፣ በቅጽበት የተቃወሙትን መደገፍ፣ የደገፉትን መቃወም፣ አመክኖ ሲጠፋ ማምታታት!

የ‹‹ሚዲያ ካውንስሉ›› ምስረታ አጨቃጫቂ ጉዳዮች ተነሱበት

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ

‹‹የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት የምክክር ጉባዔ›› በሚል የሚዲያ ካውንስ ለመመስረት እየተደረገ የሚገኘው ስብሰባ አጨቃጫቂ ጉዳዮች ተነሱበት፡፡ ለሁለት ቀን የሚቆየው ስብሰባ ዛሬ መስከረም 29/2007 ዓ.ም በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ የተጀመረ ሲሆን ‹‹የምክክር ጉባዔው››ን በሰብሳቢነት ወይዘሮ ሚሚ ስብሃቱ እንዲሁም በምክትል ሰብሳቢነት አቶ አማረ አረጋዊ መርተውታል፡፡ በጉባዔው በአብዛኛው ገዥውን ፓርቲ የሚደግፉ ሚዲያዎች፣ ማህበራትና ግለሰቦች ተገኝተዋል፡፡
mimi sibehatu
የመተዳደሪያ ደንቡ ላይ ባተኮረው የዛሬው ውይይት ካውንስሉ ‹‹የትኞቹን ሚዲያዎች ይቀፍ?›› የሚለው ጥያቄ አጨቃጫቂ ከመሆኑም በተጨማሪ የ‹‹ሚዲያ ካውንስሉ›› በበጎ አድራጎት ድርጅትነት ወይንስ በንግድ ድርጅትነት ይቋቋም የሚለውም አጨቃጫቂና ውሳኔ ያልተሰጠበት ጉዳይ ሆኖ አልፏል፡፡

በስብሰባው ላይ መንግስት ለመረጃ ዝግ መሆኑንና ይህም በጋዜጠኞች ላይ ለሚደርሰው በደል እንደምክንያት የተነሳ ሲሆን የኮምኒኬሽን ሚኒስትር ድኤታው አቶ እውነቱ ገለታ ችግሩ እንዳለ አምነዋል፡፡

‹‹የምክክር መድረኩ›› አዘጋጆች ለቅድመ ጥናትና ለጉባዔው ከእንግሊዝ ኤምባሲ የገንዘብ እርዳታ እንዳገኙ ገልጸዋል፡፡

ሆኖም አሁንም ድረስ እውቅና የተነፈገው ‹‹የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ›› በምስረታው ወቅት ከእንግሊዝ ኤምባሲ ጋር ግንኙነት ባደረገበት ወቅት በመንግስት ድጋፍ የሚንቀሳቀሱት የጋዜጠኛ ማህበራት፣ በአሁኑ ወቅት የሚዲያ ካውንስሉን ለማቋቋም በግንባር ቀደምነት የሚንቀሳቀሱት ግለሰቦችና መንግስት ‹‹ከውጭ አካላት ጋር ግንኙነት እያደረገ ነው፡፡ ይህም የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ይጎዳል›› በሚል መግለጫ ከማውጣትም በተጨማሪ በመንግስትና በመንግስት ደጋፊ ሚዲያዎች ወቀሳ እንዳቀረቡበት ይታወሳል፡፡

በነገው ዕለት ስለጋዜጠኝነት ስነ ምግባር፣ ስለ ሚዲያዎች አሰራርና መሰል ጉዳዮች ውይይት ይቀርባል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ነገረ ኢትዮጵያ መረጃዎችን እየተከታተለች ለማቅረብ ትጥራለች፡፡

ሕወሓትና በትግርኛ ተናጋሪዎች ሙሉ ቁጥጥር ስር የወደቀዉ መከላከያ ሠራዊት ከአራት አመታት በኋላ በድጋሚ ሲፈተሽ

$
0
0

Ginbot-7-Top-logo_4

ሕወሓትና በትግርኛ ተናጋሪዎች ሙሉ ቁጥጥር ስር የወደቀዉ መከላከያ ሠራዊት

ከአራት አመታት በኋላ በድጋሚ ሲፈተሽ

መስከረም  26 2007 ዓ..

ሕዝባዊ ሓርነት ወያኔ ትግራይ (ሕወሓት) ምን ያክል የኢትዮጵያን የፖለቲካ መዋቅሮች እንደሚቆጣጠር ለማወቅ በአገሪቱ የመከላከያ፣ የደህንነትና የፖሊስ ተቋሞች ዉስጥ ዋና ዋና የትዕዛዝ ሰጪና ቁጥጥር ቦታዎች ላይ በሀላፊነት የተቀመጡትን የትግራይ ተወላጆች ብዛት መመልከቱ በቂ ይመስለናል። የሕወሓት መሪዎች ስልጣን በያዙባቸዉ በመጀመሪያዎቹ ጥቂት አመታት ዉስጥ እየገነቡት ላይ ያለዉን ስርዐት መልካምና ሁሉን አቀፍ ስርዓት ለማስመሰል አንዳንድ ከነርሱ ቁጥጥር ዉጭ መተንፈስ እንኳን የማይችሉ የሌላ ብሄረሰብ ተወላጆችን አልፎ አልፎ ስልጣን ላይ አስቀምጠዋቸዉ ነበር። ዛሬ ሕወሓቶችን እራሳቸዉን እጅግ በጣም በሚያሳፍር መልኩ እነዚህ በጥንቃቄ ለቅመዉ ያመጧቸዉንም የሌላ ብሄረሰብ ተወላጆች ወደመጡበት መልሰዋቸዉ በሁሉም መስክ ቁልፍ የሆኑ የአገሪቱን  የስልጣን ቦታዎችን የሚቆጣጠረዉ የትግራይ ተወላጅ ሕወሓቶች ብቻ ሆነዋል። አያሌ ኢትዮጵያዉያን የህወሓትን አገዛዝ “ዘረኛ” አገዛዝ ነዉ ብለዉ የሚጠሩት ይህንን ሙልጭ ያለ በዘር ላይ የተመሰረተ ጭፍን አገዛዝ ተመልክተዉ ይመስለናል።

ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ ለፈጠረዉ ዘረኛ ስርዓት ብቸኛ ምሳሌ ሆኖ መቅረብ የሚችለዉ ደቡብ አፍሪካ ዉስጥ ነጮች የፈጠሩት ዘረኛ (Apartheid) ስርዓት ብቻ ነዉ። በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዉስጥ በተለይ በቁጥሩ ከፍተኛ ብልጫ ያለዉና ትግርኛ ተናጋሪ ያልሆነዉ ሠራዊት እጅግ ያኮረፈ፤ የተቆጣና ያመረረ ሠራዊት ከመሆኑ የተነሳ እራሱን የሚመለከተዉ እንደ አገር መከላከያ ሠራዊት አባል ሳይሆን አንደ ህወሓት የቤት ዉስጥ አገልጋይ ባሪያ ነዉ። ይህ የሕወሓት ዘረኞች በሠራዊቱ ላይ የፈጠሩት የመገዛትና የበታችነት ስሜት በየቀኑ ከፍተኛ ቁጣና የዉስጥ ለዉስጥ ተቃዉሞ የሚገጥመዉ ቢሆንም ህወሓት በዘረጋዉ ከፍተኛ የአፈና መረብ የተነሳ የህዝብ መነጋገሪያ አርዕስት መሆን አልቻለም። የህወሓት መሪዎችም ቢሆኑ ይህንን ቁጣና ተቃዉሞ በሚገባ ስለሚያዉቁ “ግምገማ” እያሉ በሚያዘጋጇቸዉ መድረኮች ላይ እንደዚህ አይነቶቹን በእነሱ የበላይነት ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ማስተናገድ ቀርቶ ጥያቄዎቹ እንዲነሱም አይፈቅዱም። አንዳንዴ ደፍረዉ እነዚህን ጥያቄዎች የሚያነሱ ግለሰቦች ሽብርተኛ፣ የደርግ ስርዐት ናፋቂዎች፣ ጠባብ ብሄረተኞች ወይም የጥላቻ ፖለቲካ አራማጆች የሚል ተቀጽላ ስም ይሰጣቸዋል። ዛሬ የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸዉ በተለያዩ የወያኔ እስር ቤቶች ዉስጥ የሚሰቃዩት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ለዚህ አሳዛኝ ሁኔታ የበቁት በመከላከያ ተቋሞች ዉስጥ ሠራዊቱን በየትኛዉም እርከን የሚመሩ መኮንኖች አመዳደብ ወታደራዊ አመራር ችሎታን፤ ልምድንና የብሄር ስብጥርን ያካተተ መሆን አለበት ብለዉ ደፍረዉ በመናገራቸዉ ነዉ።

ዛሬ የወያኔን መከላከያ ሠራዊት እየለቀቁ ከአገር የሚወጡ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ በመሄድ ላይ ይገኛል። እነዚህ ወታደራዊ መሪዎች፤ የበታች መኮንኖች፤ ባለሌላ ማዕረጎችችና ተራ ወታደሮች ከጠላት እንከላከላን ብለዉ የማሉላትን እናት አገራቸዉን እየለቀቁ የሚወጡት በወያኔ ጦር ዉስጥ ስር የሰደደዉ ዘረኝነትና በዚህ ዘረኝነት ላይ የተመሰረተዉ አመራር የሚያደርስባቸዉ በደል አንገፍግፏቸዉ ነዉ። በየጎረቤቱ አገር ተሰድደዉ በችግር ላይ የሚገኙ ምርጥ የኢትዮጵያ የወታደራዊ ሳይንስ አዋቂዎች ሁሉም በአንድ ድምፅ የሚናገሩት ሠራዊቱ ዉስጥ ይደርስባቸዉ የነበረዉ ንቀትና ዉርደት የሰዉ ልጅ መሸከም ከሚችለዉ በላይ መሆኑን ነዉ።

ሕወሓትን ለረጂም ግዜ የመራዉ መለስ ዜናዊና ጓደኞቹ ሥልጣን በያዙባቸዉ በመጀመሪያዎቹ ሁለትና  ሦስት አመታት ጊዜያት ቁልፍ የሆኑ ቦታዎች  ሰዎች መያዛቸዉን አስመልክተዉ ሲናገሩ ህወሓት ለ17 አመታት የደርግን አምባገነናዊ ስርዓት ሲዋጋ የፈጠረዉ ወታደራዊና ድርጅታዊ ግዝፈት አብዛኛዉ የወታደራዊና የደህንነት አመራር ቦታ በህወሓት ታጋዮች አንዲያዝ ምክንያት ሆኗል ብለዉ ከተናገሩ በኋላ ይህ አሰራር በሂደት ሙሉ በሙሉ እንደሚቀይርና የኢትዮጵያ የፖለቲካና ወታደራዊ የሥልጣን ክፍፍል የአገሪቱን ብሄር ብሄረሰቦች ጥንቅር ያገናዘበ ይሆናል ብለዉ ተናግረዉ ነበር። ሆኖም ዛሬ ይህ ከተነገረ ከሃያ አመታት በኋላና ይህንን የተናገረዉ መለስ ዜናዊ ከዚህ አለም በሞት ከተለየ ከሁለት አመታት በኋላ የሕወሓት የሥልጣን ቁጥጥር ጭራሽ አጋሽቦ ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከትግርኛ ቋንቋ ዉጭ የሌላ ቋንቋ ተናጋሪዎች ወደ ሥልጣን አይመጡም የሚባልባት አገር ሆናለች። በኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ በገነባዉ መከላከያ ሠራዊት ዉስጥ የዕዝ፤ የክፍለጦርና የመምሪያዎች አዛዥ ለመሆን ዋነኛዉ መለኪያ የትግራይ ብሄረሰብ ተወላጅና የሕወሓት ታማኝ አገልጋይ መሆን ነዉ እንጂ ችሎታ፤ ልምድ፤ ብቃትና የወታደራዊ ሳይንስ ክህሎት አይደለም። ችሎታ፤ ልምድና ብቃት መመዘኛ ሆነዉ የሚቀርቡት በመጀመሪያ ለሹመት የታጨዉ መኮንን የትግራይ ተወላጅ እና የሕወሓት ታማኝ አገልጋይ መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ ብቻ ነዉ።

የሕወሓት የስልጣን ሞኖፖሊ በወታደራዊ ደህንነት ተቋሞች ላይ ብቻ ተወስኖ አያበቃም። አብዛኛዉን የአገሪቱ የኤኮኖሚና ማህበራዊ ተቋሞችም ወይ ከላይ አለዚያም ከታች ሆነዉ የሚቆጣጠሩት የሕወሓት ታማኝ አገልጋይ ትግርኛ ተናጋሪዎች ናቸዉ። ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ለይስሙላ የተቀመጠና ከተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች የመጡ ሰዎች የሚገኝበት አገዛዝ አለ፤ በዚህ አገዛዝ ዉስጥ ደግሞ አገሪቱን ወዳሰኘዉ አቅጣጫ በዘፈቀደ የሚዘዉረዉና ከትግርኛ ተናጋሪዎች ዉጭ ሌሎች የማይገኙበት በአገዛዙ ዉስጥ ሌላ ቡድናዊ አገዛዝ አለ። ዛሬ እነ ኃ/ማርያም ደሳለኝ፤ አባዱላ ገመዳና ደመቀ መኮንንን የመሳሰሉ ምስለኔዎች ስልጣን ላይ የተቀመጡ ነገር ግን የሕወሓት ጌቶቻቸዉ ከሚነግሯቸዉ ዉጭ በራሳቸዉ ምንም አይነት ትዕዛዝ መስጠት የማይችሉ አሻንጉሊቶች መሆናቸዉን እነሱ አራሳቸዉም የተገነዘቡት ይመስላል።

ግንቦት ሰባት- የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የዛሬ አራት አመት (እ.ኤአ.በ2009) በዘር የተደራጀዉን የወያኔ መከላከያ ተቋም አደረጃጀት ምን እንደሚመስል በመረጃ አስደግፎ ለአለም ህዝብ ማቅረቡ የሚታወስ ነዉ። ግንቦት ሰባት ይህ ይሻሻላል ወይም አደረጃጀቱ በሂደት ይለወጣል ተብሎ የተነገረለት የወያኔ መከላከያ ተቋም ጭራሽ ከድጡ ወደማጡ እያዘገመ መሆኑን በጥናታዊ መረጃዎች አስደግፎ እንደሚከተለዉ ያቀርባል። በዚህ ጥናት ዉስጥ የወያኔን መከላከያ ሠራዊት ይዘትና ቅርጽ በሚገባ የሚያዉቁ፤ ሠራዊቱን ለቅቀዉ የወጡና አሁንም በሠራዊቱ ዉስጥ በማገልገል ላይ የሚገኙ ከፍተኛ መኮንኖች ተሳትፈዋል። ከዚህ ቀጥሎ የሚቀርበዉ ሠንጠረዥ የተለያዩ የመከላከያ ተቋም የስልጣን ቦታዎችን፣ በስልጣን ቦታዎችን እነ ማን እንደተቀመጡና  የተወለዱበትን ብሄረሰብም ጭምር ያሳያል።

Am1 (1)
Am2

Am3

Am4

Am5

Am6

‘አሸባሪ ብዕሮች’ (ክንፉ አሰፋ)

$
0
0

ክንፉ አሰፋ

ይህች አጭር ጽሁፍ የተወሰደችው በአውስትራሊያ ከምትታተም “አሻራ” ከተሰኘች መጽሄት ልዩ እትም ላይ ነው።

የፈረንሳዩ አንባገነን ገዥ የነበረው ናፖሊዮን ቦናፓርት በአንድ ወቅት ስለ ነጻ ፕሬስ ሲናገር “ከአንድ ሺህ ሻምላዎች ይልቅ አራት ጋዜጦች የበለጠ መፈራት አለባቸው።” ነበር ያለው።

2053fountain_pen አንባገነኖች ፕሬስን ይፈራሉ። ይጠላሉም። የህዝብ መሰረት የሌላቸው፤ በራሳቸው የማይተማመኑ ሁሉ ነጻ ሃሳብን ይጠላሉ። ነፍጥን ብቻ ተማምነው በሕዝብ ጫንቃ ላይ የሚቀመጡ፤ እንደምን ነጻ አመለካከትን ሊቀበሉ ይችላሉ?  ፍጹም አንባገነናዊነት በሰፈነባቸው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገሮች፤  ህግ አውጭው ህግ አስፈጻሚውን፣ ህግ አስፈጻሚው ደግሞ ህግ ተርጓሚውን እርስ-በርስ  የሚቆጣጠሩበት እና የሚያስተከክሉበት አካሄድ የለም። ይህንን ቁጥጥር በጥቂቱም ቢሆን ተክቶ ይሰራ የነበረው ነጻው ፕሬስ ነው። ከዚህም አልፎ ሕዝቡ መብቱን እንዲያውቅና መብቱንም እንዲያስከብር ብዙ ሰርቷል-ፕሬሱ። ሙስናን አጋልጧል፣ እንደ እንባ ጠባቂም እየሆነ የህዝብን በደልም ይፋ አድርጓል። ይህን የተቀደሰ ተግባር ማከናወን እንደወንጀል፤ ጠንከር ሲል ደግሞ እንደ ሽብርተኝነት የሚቆጠርበት ሃገር ሆናለች የዛሬይቱ ኢትዮጵያ።

መብትን ማወቅ እና ማሳወቅ፤ ‘ህዝብ ለጦርነት እንዲነሳ ማድረግ፤ ወይንም በስራዓቱ ላይ ጥርጣሬ መፍጠር  ነው’ ተብሎ ከተተረጎመ ደግሞ ጋዜጠኛን በአሸባሪነት መፈረጁ ብዙ ሊደንቀን አይገባም።

ኢትዮጵያ ላለፉት አስርት-አመታት ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ በቁጥር አንደኛ ደረጃ ላይ የነበረች ሃገር ናት።  አሁን ይህንን ደረጃዋን ለቃለች። እድገትና  ትራንስፎርሜሽኑን ተከትሎ ከመጡት ለውጦች አንደኛው መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ የአንደኝነት ደረጃዋን ያጣችው ታዲያ ትራንስፎርሜሽኑ ይዞት በመጣው መሻሻል አይደለም።  ነጻ ፕሬሱ ከሃገሪቱ እንዲጠፋ በተደረገ ሁለገብ ጦርነት እንጂ። አብዛኛው ጋዜጠኛ ተሰድዷል፣ ጥቂቶቹ ታስረዋል፣  አንዳንዶቹም  አቅማቸው ተሟጦ አልቆ፤ ዝም ብለው እንዲቀመጡ ተደርገዋል።  ለነጋሪ የተረፉትንም እስከዛሬዋ እለት ድረስ እያሳደዷቸው ይገኛሉ።

ከጅምሩ በፕሬሱ ላይ የተከፈተው የገዥው ፓርቲ ውግያ ቀላል አልነበረም። ፕሬሱ ግን እለት ተዕለት የሚያርፍበትን የአንባገነኖች ጡጫ ሁሉ ችሎ ብዙ ተጉዟል። እየተንገዳገደ፤ እየወደቀና እየተነሳ የህዝቡን የህሊና ንቃት እንዲሰፋ ከማድረጉም ባሻገር በኢትዮጵያ የማንበብ ባህል እንዲዳብር ነጻው ፕሬስ ተግቶ ሰርቷል።   የህትመት ዋጋ እስከ 500% እንዲጨምር ቢደረግም ፕሬሱ አልቆመም ነበር። ጋዜጠኞች እንደጥጃ እየታሰሩ፣ እየተደበደቡ፣  እየተሰቃዩም  ስራቸውን ላለማቋረጥ መትጋታቸውን አላቆሙም። በካድሬ ዳኞች ፍርደ-ገምድል ፍትህ ሲሰጣቸው፤  ያለ አግባብ በእስርና በገንዘብ ሲቀጡም ሰራቸውን አላቋረጡም…

የአሜሪካው ፍሪደም ሃውስ በተከታታይ ባወጣቸው ዘገባዎች ኢትዮጵያን ፕሬስ (Status: NOT FREE) “ነጻ ያልሆነች” ሃገር ሲል ፈርጇል።  የፕሬስ አዋጁንም ፍጹም አፋኝ ሲል ይከሳል። የፈረንሳዩ ሪፖርተርስ ዊዝ አውት ቦርደርስ፣ የኒውዮርኩ ሲ.ፒ.ጄ. እና የብራስልሱ አይ.ኤፍ.ጄ. በሽብር ክስ የተያዙ የጋዜጠኖችን ሰነድ እያከታተሉ አሳፋሪነቱን ቢገልጹም አፍ እንጂ ጆሮ ከሌለው ስርዓት ያገኙት የስድብ ምላሽ ብቻ ነው። አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና ሂዩማን ራይትስ ዋችም አፈናውን  ይፋ ማድረጉን ተያይዘውታል።  ከገዥው ፓርቲ የሚያገኙት ምላሽ “የኒዮ ሊበራል” አቀንቃኞች የሚል ስድብ እና ዛቻ ብቻ ነው።

ከምርጫ 97 ነኋላ ግን የህወሃት እድገት እና ትራንስፎርሜሽን፤  ጫን ያለ ነገር ይዞ ብቅ አለ።

ሽብርተኝነት!

ከዚህ በኋላ ጋዜጠኛ በህገ-መንግስት ሳይሆን፤ ህጉን በሚጻረረው አዋጅ መዳኘት እንዳለበት ተነገረ። ስርዓቱም በባሩድ ሳይሆን ይልቁንም በብእር ጫፍ እንደሚሸበር አረጋገጠ።

ይህ የሽብርተኝነት አዋጅ ቃል በቃል የተቀዳው ከአሜሪካ እና ከእንግሊዝ  መንግስታት ሰነድ መሆኑን ሃይለማርያም ደሳለኝ ለቢቢሲ ሲናገሩ ተደምጠዋል። ድንቅ ነው። ሰውየው ግን ምን እየተናገሩ እንደሆን የሚያውቁት አይመስልም። በዚህች በሙት መንፈስ የምትመራ ሃገር ሌላም ብዙ እንግዳ ነገር እንሰማለን።  የቡሽ አስተዳደር ከቶኒ ብሌየር ጋር አልቃይዳ የተባለውን አደገኛ ሽብርተኛ ለማጥፋት የነደፉት ይህ ሰነድ ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ጋዜጠኞችን ለማጥፋት እየተጠቀሙበት እንደሆነ ነው የሚነግሩን። የፈረንጆቹ ሽብርተኝነት (terrorism)  ሲተረጎም፤  “በሃይማኖት ወይንም በርዕዮተአለም ጥላ ስር ተደራጅቶ አመጽን የማድረግ ተግባር” እንደሆነ ይነግረገናል።

በሽብርተኝነት ተወንጅለው በየእስር ቤቱ የተጣሉት የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች፤ የትኛውን ርዕዮተ-አለም ወይንም ሃይማኖት ተንተርሰው አመጽ እንደፈጠሩ፣  የትኛውን አውሮፕላን እንዳስጠለፉ፣ የትኛውን ህንጻ እንዳፈረሱ፣ የትኛውን ንጹህ ዜጋ እንደገደሉ አልተነገረንም።

እርግጥ ነው። የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች እየተቹ ይጽፋሉ። ትችቱ ታድያ ለውጡ ላይ አይደለም። የለውጡ አቅጣጫ ላይ እንጂ። አቅጣጫው ትክክለኛ መስመር መያዝ እና አለመያዙን መተቸት “ወንጀል ነው” ሲባል ለቀረው አለም አዲስ ነገር ሊሆን ይችላል። ከዚያ የባሰም አለ። ገዢውን ፓርቲ መተቸት እና ስለ ለውጥ አስፈላጊነት መጻፍ በሽብርተኛነት ያስከሰሰ ወንጀል ሆኖ ሰማን። አስቂኙ ነገር፤ አዋጁ ለኦሳማ ቢን ላደን ሽብር በምእራባውያን ሀገሮች የረቀቀ የጸረ-ሽብር ህግ መሆኑ ነው።

ጋዜጠኞች በሽብርተኝነት ሲፈረጁ ነው ነጻው ፕሬስ በኢትዮጵያ አፈር የለበሰው። ይህ የመጨረሻ ጥይታቸው መሆኑ ነው። አለማቀፍ የጋዜጠኞች ተሟጋች ተቋማት ሳይቀሩ ተስፋ የቆረጡ እስኪመስል ድረድ  በዘንድሮ  አመታዊ  ዘገባቸው የኢትዮጵያን  ጉዳይ ችላ ብለውታል። እነዚህ ተቋማት በየአመቱ ስለኢትዮጵያ ፕሬስ ሁኔታ የሚያወጧቸው ዘገባዎች የሚዘገንኑ ነበሩ።  ወያኔን የማይማር፣ የደነዘዘ እና የማይለወጥ ስርዓት አድረገው ስላዩት ችላ ያሉት ይመስላል። ሃያ አመት የማይሰማ፣ ያሃ አመት የማይሻሻል፣ ሃያ አመት የማይማር ስርዓት… ውሃ ቢወቅጡት እንቦጭ ሆነባቸው።

በምርጫ 97 ሰሞን በርካታ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች ቃሊቲ ተወርውረው ነበር። በጉዳዩ ላይ  የአምነስቲ  ኢንተርናሽናል  ዲያሬክተር  ከነበሩት ዶ/ር  ማርቲን  ሂል ጋር ስናወራ አንድ ጥያቄ  አነሱልኝ።

“ለመሆኑ ሰርካለም ፋሲል ላይ ለምን እንዲህ ጨከኑባት? ”  የሚል ነበር የማርቲን ጥያቄ። እኝህ ታላቅ ሰው ይህን ጥያቄ ለምን እንዳነሱልኝ  አሁን ነው የተገለጠልኝ።

የሰርካለም ፋሲልን ጉዳይ ማንሳቱ የኢትዮጵያን ፕሬስ የሰቆቃ ጉዞ በከፊልም ቢሆን ይገልጸዋል።

ሰርካለምን ከባለቤትዋ እስክንድር ነጋ ጋር አፍነው ወደ ቃሊቲ ሲወስዷት ነብሰ-ጡር ነበረች። የመውለጃዋ ቀን ሲደርስም ከእስር አልለቀቅዋትም። በምጥ ስቃይ፣ ነብስ ውጭ፤ነብስ ግቢ ሁኔታ ውስጥ ሆና እንኳን አሳሪዎችዋ ርህራሄ አላሳዩዋትም ነበር።   በመጨረሻ እዚያው ቃሊቲ እስር ቤጥ ናፍቆትን ተገላገለች።  በዚያ የጭንቅ ወቅት የሚይዘውን እና የሚጨብጠውን ያጣ ስርዓት ምን እያደረገ እንደነበር እንኳን በውል አየውቀውም።  “የመንግስት ጠላት”  የሚል ታፔላ ተለጥፎለት የሚንቀሳቀስ ጋዜጠኛ፤ ሊወድቅ ከሚንገዳገድ ስርዓት  ከዚህም በላይ ሊደረግበት እንደሚችል ለማስረዳት ሞከርኩ።

ነብሰ-ጡርዋ ሰርካለም የተከሰሰችው ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በሃይል ለመናድ እና ለማፍረስ፣ ጥላቻን የምታስፋፋ፣ ጥርጣሬን የምትነዛ… ተብላ ነበር። በ “ምህረት” ከእስር እንደተፈታች ወደ ኬንያ ተሰደደች። በኋላም ሀገር ሰላም የሆነ ሲመስላት ከስደት ተመለሰች። ይህች ወጣት እትብትዋ ወደተቀበረባት ሃገርዋ ብትመለስም እንደዜጋ የመኖር ዋስትናዋ ግን በአንባገነኖች መዳፍ ስር ሆነ። በኑሮዋ እና በትዳርዋ ዙርያ ካለፈው የባሰ ችግር መጣባት። ባለቤትዋ እስክንድር ነጋ በሽብርተኝነት ተከሶ በፍርደ-ገምድል ዳኛ ለአመታት ተፈረደበት። ቤት ንብረታቸውም በግፍ ተቀማ። ከዚህ በኋላ በመኖር እና ባለመኖር የሚደረግ ምርጫ ውስጥ መግባት ግድ ሆነባት። እናም ባለቤትዋን ወህኒ ቤት ጥላ ዳግም ተሰደደች። እስዋም ሆነች በሰቆቃ የተወለደ ልጅዋ በመንገድ ከመወርወራቸው በፊት ያላቸው አማራጭ ይህ ብቻ ነበር።  የሚወዷት ሃገራቸውን ጥለው ከሁለት መቶ በላይ የሚሆኑ ስደተኛ ጋዜጠኞችን ተቀላቀሉ። እንደቀልድ የሚነገር ሌላም እውነታ አለ። ከ”ሽብርተኛ” ጋር በስልክም ሆነ በአካል ያወራ፣ አብሮ የታየ፣ አብሮ ሻይ የጠጣ፣ የተነካካ ሰው ሁሉ ሽብርተኛ  እንደሆነ አዋጁ ይደነግጋል። ሰርካለም እና ናፍቆት በእስር ያለው እስክንድር ጋር በሚያደርጉት ግንኙነት ሽብርተኛ ተብለው ሊወነጀሉም ይችሉ ነበር።

በስልጣን ላይ ያሉት ሰዎች ፍርሃት ውስጥ እንዳሉ ግልጽ ነው። በጋዜጠኛ የሚናድ ሀገ-መንግስት ይዘው ስንት አመት ሊዘልቁ እንደሚችሉ ባናውቅም፤ አሁንም ጋዜጠኞችን ሲያስሩ ይህንንኑ ዘፈን ይደጋግሙታል። 99.7 በመቶ በህዝብ የተመረጠ መንግስት መራጩን ሕዝብ ከቶውንም መፍራት አልነበረበትም። ነገሩ ስላቅ ነው።  ይህ ቀልዳቸው ግን የህዝቡን ንቃተ-ህሊና ዝቅ አድርጎ ከመመልከት የሚመጣ ይሁን እንጂ ጉዳዪ ሌላ ነው። አንባገነኑ ናፖሊዮን ቦናፓርት ብሎታል። ከሺ ሳንጃ አንድ ጋዜጠኛ ያስፈራል።  የጭቆና እና የአፈና ስርዓት ገንብቶ ለረጅም አመት የቆየ አንባገነን በታሪክ አልታየም።

የፈቀደውን መምረጥ የሚችልን ህዝብ አዲስ ዘመንን ብቻ እንዲያነብ መምከራቸው ብቻ አይደለም በሕዝብ ላይ ያላቸው ንቀት፤ የፍትህ ስርዓቱን ለበቀል የሚዘረጋ እጃቸው አድርገው ነጻውን ፕሬስ ለማጥፋት ሲጠቀሙበትም እጅግ ያንገበግባል።  የህግ የበላይነትን እንዲህ እያደረጉ ናዱት።

ኢሕአዴግ  የፕሬስ ነጻነትን  ለህዝቡ እንዳጎናጸፈ ይመጻደቃል።  ይህ ስህተት ነው።  መናገር፣ ሃሳብን በነጻነት መግለጽ፣ መጻፍ፣ … ወዘተ መብት የሰው ልጅ የተፈጥሮ ጸጋ እንጂ አንድ ስርዓት የሚያጎናጽፈን ጉዳይ አይደለም። በሌላ በኩል ደግሞ ይሀው ስርዓት እነዚሁኑ መብቶች እየጨፈለቀ እነሆ ሃያ ሶስት አመታትን ዘልቋል።

ነጻ ፕሬሱን ለምእራባውያን የዲሞክራሲ ማሳያ አድርጎ እንደተጠቀመበት እርግጥ ነው። የአለም ባንክ እና ለጋሽ ሃገሮች በኢትዮጵያ የሳንሱር አዋጅ እንደጠፋ ነው የሚነገራቸው። የእርዳታና ብድር እጃቸውን የሚዘረጉልንም ከቀድሞው የተሻለ የመጻፍና የመናገር ነጻነት አለ ብለው ስለሚያምኑ ይመስላል። ግና ይህ የሳንሱር አዋጅ በአእምሮ ሳንሱር መተካቱን  የምናውቀው እኛ ብቻ ነን። ሳንሱር ቢኖር ይህ ሁሉ ጋዜጠኛ ባልታሰረ፣ ባልተንከራተተ እና ባልተሰደደ ነበር።

ምርጫ መጣ! ጋዜጠኛ ይውጣ! እንዲሉ… በቅርቡ በስድስት ነጻ ፕሬስ ህትመቶች ላይ ከተመሰረተው ክስ ጋር በተያያዘ  አስራ ሁለት ጋዜጠኞች ለስደት መብቃታቸው ተዘግቧል። በጭላንጭል የነጻነት ድባብ ይንቀሳቀሱ የነበሩት፤ አዲስ ጉዳይ፣ ሎሚ፣ ጃኖ፣ አፍሮ ታይምስ እና እንቁ ጋዜጦች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ጋዜጠኞቹም በአሸባሪነት ሽፋን ተከስሰው  እስከ አስራ ስድስት አመት የሚደርስ ጽኑ እስራት ተበይኖባቸው የነእስክንድር ነጋ፣ ውብሸት ታዬ እና ርእዮት አለሙ እጣ ይደርሳቸዋል። እነዚህ ጋዜጠኞች የነበራቸው አማራጭ የሽብር አዋጁ ሰለባ መሆን አልያም አገር ለቀው መሰደድ ነው። ተሰደዱ።  የስደተኛ ጋዜጠኛውን ቁጥር ወደ 210 አሳደጉት።

ውንጀላው ግን በተያዘለት መርሃ-ግብር ቀጥሏል።  ሰሞኑን “ያልተገሩ ብዕሮች” በሚል ርእስ በኢቲቪ የቀረበውን “ዘጋቢ ፊልም” ያስተውሏል?  በአንድ በኩል የጋዜጠኖቹ ጉዳይ በህግ የተያዘ እንደሆነ ይነግሩናል። በሌላ በኩል ደግሞ “ልማታዊ” ተዋንያን እና የስርዓቱ አጎብዳጆችን በመገናኛ ብዙሃን አቅርበው ፍርድ እንዲሰጡ ያደርጓቸዋል። በእርግጥ በመገናኛ ብዙሃን እየቀረቡ አንድ ተጠርጣሪን በወንጀለኝነት መፈረጅ አዲስ ነገር አይደለም። የፍትህ አካሉ ውሳኔ ከመስጠቱ  በፊት ተጠርጣሪው በኢቲቪ የፖለቲካ ፍርድ ይበየንበታል።  ከዚያም እንደ “ዳኛ” ልዑል አይነት የሲቪል ሰርቪስ ምርቶች ውሳኔውን ያጸኑታል።

በዚያ የኢቲቪ ቅንብር ሃይሌ ገብረስላሴም ተዋንያን ነበር።  የሚናገረውም የትዬለሌ። “ትልቁ የጦር መሳርያቸው ፕሬስ ነው።… ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው ይባላል… ” ይለናል ሃይሌ ገብረስላሴ። “ዘጋቢ” ፊልሙም  የእነ እስክንድር ነጋን ፎቶ፣ የእነ ተመስገን ጽሁፎች ያሳየናል። የዚህ ድራማ ሌሎቹ ተዋንያን ከሙያው ጋር የተያያዝን ነን የሚሉ አድርባዮች ናቸው። ሃይሌ ግን ምን ቤት እንደሆነ ግልጽ አይደለም።  በየትኛውስ እውቀቱ ነው ፍርድ ሊሰጥ የደፈረው? “አንድ ጋዜጣ  የውሃ አምራች ድርጅትን እንዲዘጋ አድርጓል።”  ሲል ሃይሌ በዚያ “ዘጋቢ ፊልም” ይወነጅላል። አንድ ጋዜጠኛ እውነትን ጽፎ  የንግድ ድርጅትን ወይንም የመንግስት ተቋምን ማፍረስ ወይንም በተቋማቱ ላይ ጥርጣሬ መፍጠር ከቻለ እንዲያውም ጀግና ነው የሚባለው። ጋዜጠናው የሚጽፈው ውሸት ከሆነ ደግሞ ፍርዱን ለህዝቡ ለምን አይተውለትም?

አብራሃ ደስታ ሌላው በአሸባሪነት ሽፋን የተከሰሰ ጋዜጠኛ ነው።  አብርሃ አሸባሪ መሆኑ የተረጋገጠው ፍርድ ቤት ሲገባ እና ሲወጣ ነው።  ሲገባ በጭብጨባ ሲወጣ በጭብጨባ ተሸኝቷል። ህዝብ በነቂስ ወጥቶ  ኣብርሃ ጀግና! የነፃነት ታጋይ! እንወዳሃለን፤እናከብርሃለን ሲለው እነ ሃይሌ ገ/ስላሴ የት ነበሩ?

ያልተገራ አንደበታቸውን በመገናኛ ብዙሃን ሲከፍቱ የነበሩት እነዚህ ተዋንያን የሚነግሩን እጅግ አሳፋሪ ነገር ነው።  አጠቃላይ ይዘቱ በመንግስት ላይ ምንም አይነት ትችት መቅረብ የለበትም የሚል እንድምታ አለው። የህወሃትን አንባገነናዊነት መተቸት፣ የስርዓቱ ፖሊሲዎች መንካትና በባለስልጣናቱ ላይ ጥርጣሪ እንዲኖር ማድረግ… ስርዓቱን ያፈርሰዋል ነው እያሉን ያለው።  ህግ አውጭው ከህግ አስፈጻሚውን፣ ህግ አስፈጻሚው ደግሞ ህግ ተርጓሚውን እርስ-በርስ  የሚቆጣጠሩበት እና የሚያስተከክሉበት አካሄድ በሌለበት ሃገር ነጻው ፕሬስ ከዚህ ውጭ ምን ይስራ ነው የሚሉት? ፕሮፓጋንዳ?

ለፕሮፓጋንዳውማ በርካታ አማራጮሽ አሉ። አዲስ ዘመን ጋዜጣም አለልን። ለ90 ሚሊዮን ህዝብ የቀረው ጋዜጣ።  አዲስ ዘመን  በቁጥር ስንት ሺ እንደሚታተም ባናናውቅም በኪሎ እየተሸጠ የሸቀጥ እቃ መጠቅለያ ሆነ እንጂ።  ‘የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተመረቁ፣ ሃይለማርያም ደሳለኝ ወደ ሱዳን ሄዱ፣ ሃይለማርያም ደሳለኝ ከሱዳን ተመለሱ። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ 11 እጅ እንደሚያድግ ሃይለማርያም ደሳለኝ ተናገሩ።’  …. የሚሉ ዘገባዎችን እየያዘ ከሸቀጥ እቃ መጠቅለያነት ውጭ ለሚመጻደቁለት እድገት ምንም እንዳልፈየደ እንኳ አያውቁትም።

የመገናኛ ብዙሃን አፈናው በነጻ ፕሬሱ ላይ ብቻ አልተገደበም። በኢትዮጵያ የመረጃ መረቦችም ታፍነዋል።  ከሰብ ሰሃራ አፍሪካ በኢንተርኔት ይዞታ እና አገልግሎት የመጨረሻዋ ሃገር ናት። ኢንተርኔቱን የሚቆጣጠረው መንግስታዊው ቴሌኮም ስርዓቱን የሚተቹ ድረ-ገጾችን በቻይና ቴክኖሎጂ እንዲዘጉ አድርጓል።  የዜጎችን ስልክ በህገወጥ ማንገድ መጥለፍ የተለመደ ተግባር ነው። እንዲሁም ስካይፕ እና ቫይበር ያሉ የቮይስ ኦቨር ስልኮች ደግሞ ፊን ፊሸር በተባለ የኮምፒዩተር ቫይረስ አማካኝነት ይጠለፋሉ።  እንዲህ እያሉ በዜጎች የግል ህይወት ሳይቀር እየገቡ ቴሌን ሙሉ በሙሉ የስለላ ተቋም እንዳደረጉት የአሜሪካው ሂዩማን ራይትስ ዋች ይፋ አድርጓል።

ኢትዮጵያን ወደ ጨለማ ዘመን እየወሰዳት ያለው ይህ የህወሃት ስርዓት የኢንተርኔት ተጠቃሚው  እንዲያሽቆለቁል እየጣረ እንደሆነ ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት። በተለይ የፌስቡክ አብዮትን ለመግታት ስለሚሻ የኢንተርኔት አገልግሎትን ማዳከሙ ላይ ጥብቅ አቋም ይዟል። መንግስት አልባዋ ሶማልያ እንኳን፣  ስድስት የቴሌፎንና ስልክ አቅራቢ ኩባንያዎች አሏት። በዚህ ቀላል ቴክኖሎጂ እንኳን ከሶማልያ በታች ሆኖ ስለ እድገት መመጻደቃቸው ሊያፍሩበት ይገባል።

እጅግ የሚያሳዝነው ይህ ስርዓት ለፈጸመው ለዚህ ሁሉ በደል ለሽልማት መብቃቱ ነው። ልማታዊው አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ በአርቲስቶች ስም ለሟቹ ጠቅላይ ሚ/ር የወርቅ ብዕር ነበር ያበረከተላቸው። ብዕር ትልቅ ትርጉም አለው። ብእር የሚሸለም ሰው ለፕሬስ ክብር ያለው፤ ፕሬስን የሚያከብር ሰው ነው። ሰራዊት የወርቅ ብዕር እንዲሸልም አርቲስቶች አልወከሉትም ነበር።  ይህንን ሲያደርግ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች እስር ቤት ውስጥ ይንገላቱ ነበር። ሰራዊት ይህንን ሲያደርግ  የአለም አቀፍ ህብረተሰብ ጠ/ሚኒስትሩን የፕሬስ አፈና በእጅጉ ያወግዝ ነበር።   እንደ ሰራዊት ያሉ ሃላፊነት የጎደላቸው ሰዎች ብዙ አይደሉም።  ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው ሲሉ እንዲህ አይነት ስራ እየሰሩ በሰው በቁስል ላይ እንጨት ይሰድዳሉ። ታዲያ እንደነዚህ አይነቶቹ አድርባዮችም ለፕሬሱ መጥፋት ሚናቸው ቀላል አይደለም። የማያልፍ የለም። ሁሉም ያልፋል። መንግስትም እንደ አንሶላ ተጠቅልሎ ይሄዳል። ይህ ቀን አልፎም ለትዝብት ያበቃናል።

ማን ነበር “ፕሬስ  የሌለው መንግስት ከሚኖረን  መንግስት የሌለው  ፕሬስ  ቢኖረን  እንመርጣለን።” ያለው? እርግጥ ነው። ያለ ፕሬስ የሚኖር ህዝብ በጨለማ ነው የሚጓዘው። ያለ ነጻ አስተሳሰብ እና ያለ ነጻ ፕሬስ፣  እድገት ይመጣል ማለት አይታሰብም። እንዲያው የህዝብን ንቃተ-ህሊና ዝቅ አድርጎ መመልከት ይሆናል እንጂ።

Health: ‹‹ኦሜጋ – 3››: የስኳር እና የልብ በሽታዎችን ጨምሮ ለ7 የተለያዩ በሽታዎች ተፈጥሯዊ መፍትሄ

$
0
0

ኦሜጋ-3 ፋቲ አሲድ (Omega-3 fatty acid) ከቅባት ዝርያዎች አንዱ ሲሆን በጣም አስፈላጊ ከሆኑት የቅባት ዘሮችም እንደ አንዱ ይቆጠራል፡፡ ኦሜጋ-3 ለሰዎች ጤንነት እጅግ አስፈላጊ ጠቃሚ የመሆናቸው ያህል በሰውነታችን ውስጥ ግን መመረት አይችሉም፡፡ ስለሆነም እኒህን የቅባት ዘሮች ማግኘት የምንችለው ከምግብ ብቻ ነው፡፡ የዚህን አይነት ቅባት (ኦሜጋ-3) በአሳ ዘይት፣ በአሳ፣ በቱና እና በሌሎችም የባህር ምግቦች ውስጥ ይገኛል፡፡ ይህ ኦሜጋ-3 የተባለ የቅባት ዘር ለሰውነት በጣም አስፈላጊ እንደሆነ የተለያዩ ጥናቶች ያረጋግጣሉ፡፡ ይህም የአዕምሮን አሰራር እጅግ ከማጎልበቱም በላይ ለህፃናት አካላዊ ዕድገትም ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ የአሜሪካ የልብ ማህበር (American heart association) ቢያንስ በሳምንት ከሁለት ጊዜ ላላነሰ የአሳ ምግቦችን በመመገብ ሊከሰት ከሚችል የልብ በሽታ ራስን መከላከል እንደሚቻል አበክረው ይገልጻሉ፡፡ ኦሜጋ-3ን በመመገብ የተለያዩ እንደ ልብ በሽታ፣ ካንሰር እና የመገጣጠሚያ ህመሞች ያሉ ስር ሰደድ በሽታዎች ሊያመጡ የሚችሉ አጋጣሚዎችን መከላከል ይቻላል፡፡
omega 3 source

ከሰውነታችን ክፍሎች ኦሜጋ-3ን በአብዛኛው የሚጠቀሙት የነርቭ ሴሎች ናቸው፡፡ የአዕምሮአችን ይህም በአዕምሮአችን አሰራርና በባህሪያችን ላይ ትልቅ ተፅዕኖ እንደሚያመጣ እሙን ነው፡፡ ገና የሚወለዱ ህፃናትም ይህን ኦሜጋ-3 የተባለ ቅባት ወይ በፅናታቸው ማህፀን ውስጥ አሊያም ከተወለዱ በኋላ ደግሞ በአሳ ዘይት መልክ ተዘጋጅቶ የሚሸጠውን ፈሳሽ ቅባት ካላገኙ የእይታ ወይም የነርቭ ችግር ሊያጋጥማቸው ይችላል፡፡ የኦሜጋ-3 እጥረት በተለይም በድካም፣ አነስተኛ የማስታወስ ችሎታ፣ የቆዳ መድረቅ፣ ከልብ ጋር ተያያዥ የሆኑ ችግሮች፣ የአዕምሮ አስተሳሰብ መዋዠቅን (Mood swing)፣ የድብርትንና ደካማ የሆነ የደም ዝውውርን በማምጣት ይታወቃሉ፡፡

በመቀጠል የኦሜጋ-3 ቅባት ለሰውነታችን የሚያበረክታቸውን በርካታ ጥቅሞች አንድ በአንድ እናያለን፡፡ ምንም እንኳን ኦሜጋ-3 ቅባቶች በተለየ ሁኔታ የልብ በሽታን እንደሚከላከሉ ቢታወቅም ከዚያም አልፎ ተርፎ ግን ለተለያዩ ሌሎችም በሽታዎች እንደሚጠቅሙ የተለያዩ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡

የኮሌስትሮል መጠንን ለመቆጣጠር

በአብዛኛው የባህር ምግብ የሚመገቡ ግለሰቦች የደማቸው የኮሌስትሮል መጠን እጅግ ጤነኛ ነው፡፡ ይህን ለማረጋገጥም በሜዲትራኒያን አካባቢና በአንታርክቲክ የሚኖሩ ግለሰቦች ላይ የደማቸው የኮሌስትሮል መጠንን የሚመለከት ምርመራ ተደርጎ የነበረ ሲሆን በውጤቱም በሁለቱም አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ግለሰቦች እጅግ ጤነኛ የሚባል የኮሌስትሮል መጠን በደማቸው ውስጥ ተገኝቷል፡፡ ይህን ኦሜጋ-3 የተባለ ቅባት በምግብነት በመጠቀም የኮሌስትሮል መቸመርን መከላከል ብቻ ሳይሆን ሙሉ ለሙሉ መቀነስም ይቻላል፡፡

ከፍተኛ የደም ግፊት

ከፍተኛ የደም ግፊት ባለባቸው ግለሰቦች ላይ በተደረገ ተከታታይ ጥናት በኦሜጋ-3 ቅባት የተቀመመ ምግብን አዘውትረው የሚመገቡ ግለሰቦች ላይ የደም ግፊታቸው የቀነሰ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ከፍተኛ የደም ግፊት ያባቸው ሰዎች ላይ በየቀኑ ከ3 ግራም በላይ ኦሜጋ-3 ቅባትን በመውሰዳቸው ብቻ የደም ግፊት መጠናቸው በእጅጉ ሊቀንስ እንደሚችል ይታወቃል፡፡
የልብ በሽታዎች

የልብ በሽን መከሰት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቅባት መጠናቸው አነስተኛ የሆኑ ምግቦችን መመገብ ይመከራል፡፡ እኛ የምንመክረው ደግሞ የቅባቱን አይነት በመቀየር እንደ ኦሜጋ-3 ያሉ ብዙም ጉዳት የሌላቸውን ቅባቶች በመጠቀም የቅባት ክምችትን ማስቀረት ይቻላል እንላለን፡፡ በአሳ ዘይት ውስጥ የሚገኙት የቅባት አይነቶችም ለልብ በሽታ አጋላጭ የሚሆኑትን እንደ ኮሌስትሮልና ከፍተኛ የደም ግፊት በሽታን መከሰት በማስቀረት ግለሰቡ የልቡን ጤና እንደተጠበቀ እንዲቆይ ይረዳሉ፡፡ በተጨማሪም እነዚህ ቅባቶች የደም ስር መጥበብንና የደም መርጋትን ስለሚከላከሉ በተዘዋዋሪ የልብን ጤንነት ይጠብቃሉ፡፡ በዚህ ዙሪያ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩትም በየቀኑ የአሳ ዘይት የሚመገቡ ግለሰቦች የልብ በሽታ ቢኖርባቸውም እንኳን በተደጋጋሚ የመታመም እድላቸው እጅግ አናሳ ሲሆን የአሳ ዘይት ከማይመገቡት ይልቅ የመሞት ዕድላቸውም የዚያኑ ያህል አናሳ ነው፡፡ የአሳ ዘይት ከዚህም በተጨማሪ በደም መርጋትና ወደ አዕምሮ ደም የሚያደርሱት የደም ስሮች በቅባት በመደፈን የሚመጣውን የስትሮክ በሽታ መከሰትን ይቀንሳል፡፡ ከላይ እንደጠቀሱትም በሳምንት ቢያንስ ከ2 ጊዜ ያላነሰ የአሳ ምግብ የምንመገብ ከሆነ የስትሮክን መከሰት እስከ 50% በሚደርስ ልንቀንሰው እንችላለን፡፡

ለስኳር በሽታ

በስኳር በሽታ የተጠቁ ግለሰቦች ከፍተኛ የሆነ የትራይ ግላይሴራይድ እና በጣም ዝቅተኛ የሆነ የሃይዴንሲቲ ሊፒድ መጠን በደማቸው ውስጥ አለ፡፡ ከአሳ ዘይት የምናገኘው ኦሜጋ-3 ቅባትም በደማችን ውስጥ ያለውን የትራይግላይ ሴራይድ መጠን የሚቀንሰው ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ የሀይዴንሲቲ ሊፒድ መጠንን ይጨምረዋል፡፡ ስለሆነም የስኳር በሽታ ታማሚዎች የኦሜጋ-3 ቅባትን በመመገብ የስኳር መጠናቸውን ማስተካከል እንደሚችሉ ይታወቃል፡፡

የመገጣጠሚያ ህመሞች
omega 3

በዛ ያሉ ጥናቶች የሚያሳዩት የኦሜጋ-3 ቅባት እንደ ምግብነት ስንጠቀምባቸው በመገጣጠሚያችን ላይ ሊከሰቱ የሚችሉ ህመሞች በተለይም የሪህን በሽታን የህመም ስሜት ለመከላከል ይረዳል፡፡ በዚሁ ዙሪያ የተሰሩ የተለያዩ ጥናቶች እንደሚያሳዩትም የኦሜጋ-3 ቅባቶች የመገጣጠሚያ መላቀቅን፣ የጠዋት ጠዋት ህመሞችን በማስታገስና ለሪህ በሽተኞች ደግሞ የሚወስዱትን የመድሃኒት መጠን እንዲቀንሱ በማድረግ ከማስታገሻነት ያገለግላል፡፡ በተጨማሪም ይህ የቅባት አይነት ከተለዱት የህመም ማስታገሻ መድሃኒቶች ጋር በመቀናጀት በሪህ አማካኝነት ለሚመጡ የመገጣጠሚያ ህመሞችና ለሆድ ህመም በመድሃኒትነት ያገለግላል፡፡

ለአጥንት መሳሳት

በተለያዩ ታማሚዎች ላይ በተደረገ ጥናት የኦሜጋ-3 ቅባቶች በሰውነታችን ውስ ያለ የካልሲየምን መጠን በመጨመር የአጥንታችን ጥንካሬ እንደተጠበቀ እንዲቆይ ያደርገዋል፡፡ የዚህን ኦሜጋ-3 የተባለ የቅባት ወይም የሌላ እጥረት ያለባቸው ሰዎች በአጥንት መሳሳት በሽታ የመጠቃት እድላቸው የቅባት መጠናቸው ልከኛ (Normal) ከሆኑት ይልቅ ሰፊ ነው፡፡ የአጥንት ጥንካሬ በመጨመሩ ረገድ የኦሜጋ-3 ጥቅም የሚጎላው ዕድሜአቸው በገፉት ሰዎች ላይ ነው፡፡

ለድብርት በሽታ

ሰዎች በምግባቸው ውስጥ የኦሜጋ-3 ቅባት በቂ ካልሆነ በድብርት የመጠቃት ዕድላቸው እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ የኦሜጋ-3 የቅባት የነርቭ ሴል ሜምብሬንን ከሰሩት ወሳኝ ንጥረ ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ይህም ነርቭ ሴሎች እርስ በርሳቸው በብቃት መልዕክት እንዲለዋወጡ ትልቅ እርዳታ ያደርጋል፡፡ ይህም አእምሮአዊ ጤንነት እንደተጠበቀ እንዲቆይ ስለሚያደርግ የእነሱ ማነስ በግለሰቡ የስነ ልቦና ሁኔታ ላይ ታላቅ ተፅዕኖን ያሳርፍበታል፡፡
በድብርት ተጠቅተው ሆስፒታል ከገቡ ግለሰቦች አብዛኞቹ የሰውነታቸው የኦሜጋ-3 የቅባት መጠን እጅግ ያነሰ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በድብርት ለተጠቁ ሰዎች በሳምንት ከ2-5 ጊዜ የሚደርስ የአሳ ምግብ ለ5 ዓመት እንዲመገቡ ከተደረገ በኋላ የድብርትም ሆነ የጥላቻ ስሜታቸው ፍፁም እንደጠፋ ይጠቀሳል፡፡

ኦሜጋ-3 ከምን አይነት ምግቦች ውስጥ ይገኛል?

ኦሜጋ-3 ቅባትን ከአሳ፣ ከአትክልትና ከለውዝ በዋናነት ማግኘት ይቻላል፡፡ በዝርዝር ለመጥቀስም ሰርዲን፣ ቱና እና ፍሬሽ የአሳ ውጤቶች ላይ የሚገኝ ሲሆን ከተክሎች ደግሞ በሶያ ፍሬ፣ በሶያ ዘይት ከዱባ ፍሬ ውስጥ በዱባ ፍሬ ዘይት በለውዝና የለውዝ ቅቤ ውስጥ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም የአሳ ዘይት ‹‹Code-liver oil›› በፋብሪካ ተመርቶ በገበያ ላይ ይሻጣል፡፡


‹‹በሚዲያ ካውንስሉ›› መንግስት ይግባ መባሉ አከራከረ

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) ‹‹የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት የምክክር ጉባዔ›› በሚል የሚዲያ ካውንስ ለመመስረት እየተደረገ በሚገኘው ስብሰባ መንግስት ይግባ መባሉ አከራካሪ ሆኗል፡፡ ለሁለት ቀን የሚቆየው ስብሰባ ትናንት መስከረም 29/2007 ዓ.ም በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ የተጀመረ ሲሆን ‹‹የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት የምክክር ጉባዔ›› በሚኖረው 15 የቅሬታ ሰሚ አባላት የመንግስት ተወካይ ሊኖር ይገባል መባሉ ተቃውሞ አስነስቷል፡፡ በእነ ሚሚ ስብሃቱ የሚመራው አደራጅ ኮሚቴ ቅድመ ጥናቱ ላይ ‹‹የመንግስት ተወካይ መኖር አለበት›› ብሎ ቢያቀርብም ከተሰብሳቢዎቹ መካከል ‹‹የመንግስት ተወካይ ካለ መንግስት ማህበሩን ይቆጣጠረዋል›› በሚል ቅድመ ጥናቱን ተቃውመዋል፡፡ ‹‹የመንግስት ተወካይ ይኑር አይኑር›› የሚለው ክርክር ረዥም ጊዜ የፈጀ ሲሆን ውሳኔ ሳይሰጥበት ታልፏል፡፡
Lomi-magazine-
በተመሳሳይ የገቢ ምንጩ ከየት ይሁን የሚለው አጀንዳም አከራካሪና ውሳኔ ያልተሰጠበት ሲሆን አደራጅ ኮሚቴው በቅድመ ጥናቱ የ‹‹ዴሞክራሲ ፈንድ›› በሚል የገቢ ምንጩ ከመንግስት መሆን እንዳለበት አስቀምጧል፡፡ በሌላ በኩል ግን ተሰብሳቢዎቹ ካውንስሉ ነጻ ሆኖ መቀጠል ካለበት አባል የሚሆኑት ሚዲያዎች በሚያዋጡትና በሌሎች መንገዶች በሚሰበሰብ ገቢ መቀጠል እንዳለበት፣ የገንዘብ ምንጩ ከመንግስት ከሆነ መንግስት ሊቆጣጠረው እንደሚችል ተከራክረዋል፡፡

ወይዘሮ ሚሚ ስብሃቱና ባለቤቷ አቶ ዘሪሁን ተሾመ የሚመሩት ቡድን የመንግስት ተወካይ በቅሬታ ሰሚው መካተት አለበት፣ ‹‹የዴሞክራሲ ፈንድ›› በሚል የገቢ ምንጩ ከመንግስት መሆን አለበት በሚል የተከራከሩ ሲሆን የፎርቹን ጋዜጣ ባለቤት አቶ ታምራት ገ/ጊዎርጊስንና ሌሎች በስብሰባው የተገኙ የሚዲያ ባለቤቶችና ተወካዮች ከእነ ሚሚን አቋም በተቃራኒ ቆመዋል፡፡ በሁለቱ አከራካሪ ጉዳዮች ምክንያት ዛሬ መስከረም 30/2007 ዓ.ም በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ ይደረጋል ተብሎ የነበረው ፕሮግራም ለሰዓት ተላልፏል፡፡

ካውንስሉን ለማቋቋም የቅድመ ጥናት ያደረጉት የገዥውን ፓርቲ አቋም የሚደግፉና በገዥው ፓርቲ የሚደገፉ ሚዲያዎች ሲሆን በስብሰባውም የእነዚህ አካላት አቋም ጎላ ብሎ ተንጸባርቆበታል፡፡

ትምክህተኛና ጠባብ ማን ነው? –ከአስገደ ገ/ስላሴ መቀሌ

$
0
0

አቶ አስገደ ገ/ስላሴ

አቶ አስገደ ገ/ስላሴ

የህወሓት ኢህአደግ መንግስት ፖሊሲና ስትራተተጂ ስልጠና በሚል ሽፋን ተማሪዎች በሃገር ደረጃ ከ300 ሺ በላይ የፍትህ አካላት ማለት ዳኞች ቸቃብያን ሕግ ፖሊሶች በሙሉ መጀመርያ በየ ክልሉ ለ15 ቀናት ስልጠና ተሰጣቸው በተለይ በትግራይ የፈትህ አካላት በውቅሮ 15 ቀን በአክሱም ከዛ በላይ እየሰለጠኑ ይገኛሉ::

በዚሁ ስልጠና በሁሉም ቦታ ማለት ይቻላል:: የድሮ ነገስት በማንሳት በፊሊም የተቀረፀ እነዛ ነገስታት የትምክህትና የጠባብነት ምንጭ መሆናቸው:: ሃገራችን ዘር ሃይማኖት ቢሄር ከቢሄር እያጋጩ የትምክህትና ጠባብነት መፈንጫ አድርጎዋታል በማለት ሲያማርሩ ከርመዋል:: በሌላ በኩል የህወሓት ኢህአደግ መንግስት ካለፉት ስርዓቶች የበለጠ ሃገራችን እንደቀየረ ሲነግሩን ከርመዋል::

በተሰብሳቢዎች ግን የምትነግሩን ያላቹሁ በንቃተህልናቸው አሁን ካለው ትውልድ እጅጉን የወረዱ ነበሩ:: ያም ሆኖ ሃገራችን አንድነቷና ሉኦላዊነቷ ጠብቃ እንድትኖር አድርጓታል:: እናንተ ግን የዚህች ሃገር ሉኦላውነቷ ያስደፈራቹሁ ናቹሁ:: ኢትዮዽያ የባህር በሯን አሳልፋቹሁ ሰጥታቹሁ በሁሉም ነገረ ጠገኛ አድርጋቹሁን አላቹሁ ሃገራችን በቋንቋ በወንዝ እንድትከለልና ዜጎች በፈለጉት በሃገራቸው ክልል ሰርተው እንዳይኖሩ በማደረግ ጠባብነና ትምክህት እንዲነግስ ከማድረጋቹሁ አልፎ የሃይማኖት የቢሄር ግጭት ተስፋፍቶ ዜጎች እርስ በእርሳቸው እንዳይተማመኑ አድርጋቹሁ እነ አፀይ ዩሃንስ አፀይ ምንሊክ የቴክኖሎጂ እውቀት ባልነበረባቸው ምንም እንኳ አንዳንድ ስህተቶች ቢኖሩዋቸው እቺ ሃገረ ስትደፈር የኢዮዽያ ህዝብ እንደ አንድ ሰው ሆኖው ሕብርና ሃገራዊ ወኔን በመፍጠር ሃገራችን ከባዕድ ወረራ ተከላክለው አቆይቶውናል:: እናንተ ግን በጥቂት የፓርቲ አመራር ውሳኔ ብዙ ስህተት ፈፅማቹሃል:: በተጨማሪም ለህዝቡ ይሁን ለመንግስት ሰራተኛ በአንድ ወጥ በማስተማር ፈንታ የትግራይና የኦሮሞ ህዝብ የአፀይ ምንሊክ መጥፎ ገፅታ በፊልም በማሳየት በአማራም በኦሮሞ ወይም የትግራይ ነገስታት መጥፎ ገፅታ በማሳየት በሌሎች ቢሄሮች ቢሄረሰቦችም እንደዚሁ እንዲናናቁ አድርጋቹሃል ተብለዋል::
በኔ እምነትም ትምክህትና ጠባብነት እንዲስፋፉ የሚያባብሱት ያላቹሁ የህወሓት ኢህአደግ መሪዎች ናቸው:: ስለዚህ ትምክህተኛና ጠባብ ማንው ለሚለው መልሱ ኢህአደግ ነው:: ይህ ደግሞ የኢህአደግ መሪዎች ሕብረተሰቡ በትምክህትና ጠባብነት ስሜት ካልከፋፈሉት ስልጣናቸው እድሜ የለውም:: ሌላ የኢህአደግ መሪዎች የትምክህት ቋት መሆናቸው መረጋገጫ በዚህች ሃገር ከኛ ፖለቲካዊ አስተሳሰብ (አይዶሎጂ) ወዲያ የለም ከነሱ እምነት ውጭ የራሱን ሃሳብ ይዞ የተነሳ ፓርቲ ወይም ቡድን ወይም ግለሰብ እንቢ ላለ ሰው ጥይት አጉርሰው ነው መልሱ:: ሌላ ቀርቶ የሃገራችን የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ እየተነተኑ ለህዝብ መረጃ የሚያደርሱ ጋዜጤኖች አምዳውያን የደሀረ ገፅ ጦማርያን የፓርቲ መሪዎች ከሃገር ውጭ እንዲሰደዱ በወህኒ ቤት ታስረው እንዲበሰብሱ ሌሎችም ተሸማቅቀው እንዲኖሩ ተደርገዋል እየተደረጉን ናቸው::

መላው የኢትዮዽያ ህዝብ ሙሁራን ተማሪዎች የመንግስት ሰራተኖች የህወሓት ኢህአደግ መሪዎች አሰተሳሰብ ካልተቀበለ ከሁሉም የስራ እድል ጥቅማ ጥቅም የማግኘት ነፃ ሆኖ እንዳይንቀሳቀስ ተደርገዋል ድርጊቱ እየቀጠለ ነው:: አሁንማ የኢትዮዽያ ህዝብ የመሬት ባለቤትነቱ ተነጥቆ የኢሀአደግ መሪዎች ጢሰኛ (ተጠማኝ) እንዲሆን ተደርገዋል:: የሃገሪተቱ አበዛኛው ብዙ ገንዘብ ሊያስገኙ የሚችሉ የእንድስትሪ ማእከላት በኢሀአደግ መሪዎች ጠፍረው በመያዝ የግል ባለሃብቶች እንዲቆረቁዙ አድርጎዋቸዋል:: በሌላ በኩል የሞያ የሰራተኛ የሴቶች የወጣት ማሕበራት የእምነት ተቋማት በሙሉ የኢህአደግ አደረጉዋቸው:: እምነቶች በመመርያ ካልተጓዙ የማይኖሩበት ሁኔታ ተፈጥረዋል::

የተቃዋሚ ፓርቲዎች በአስሳሰብ የላቁ ሆኖው ካልተገኙ አስተሳሰባቸውን በሰላማዊ ውድድር እንደማሸነፍ መጥፎ ስሞች በመለጠፍ ትምክህተኛ ፈላጭ ቆራጭ ሕግ በማፅደቅ እንዲደቁ ተደርገዋል እየተደረጉ ይገኛሉ:: በዚሀ ምክኒያት የህወሓት ኢህአደግ ፓርቲ በፈጠረው የጠባብነት ባህሪያትና ተግባር ጠንቅ ብዙ የተቃዋሚ ኃይሎች ነፍጥ አነሱ ልክ ትምክህተኛው ህወሓት ወደ ስልጣን በመጣበት መንገድ ስልጣን ለመያዝ በረሃ ገብተዋል እየገቡም ይገኛሉ:: ሌሎችም በአሸባሪነት ሰበብ በየ ወህኒ ቤቱ ታጉረዋል:: የዚህ አደጋ ውጤት የህወሓት መሪዎች ከደርግና ሌሎች መንግስታት ትምክህትና ጠባብነት ከፈጠሩት ተሞክሮ እንደማሻሻል ፈንታ የባሰው ትምክህተኛ ጠባብነት አንግሰዋል:: ለዚህ ጉዳይ ቆም ብለው አስበው ሰክነው በሰላም ካልፈቱት ሃገራችን ኢትዮዽያ ከባድ አደጋ እያንጃበባት ነው:: ለሚፈጠረው አደጋ ደግሞ ተጠያቂዎች የህወሓት ኢህአደግ መሪዎች ናቸው:: የኢትዮዽያ ህዝቦች እንደሆን በቦታችን ነን አንበረከክም::

በጉራፈርዳ ወረዳ 25 አማሮች መገደላቸው ተሰማ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በደቡብ ክልል በቤንች ማጅዞን በጉራፈርዳ ወረዳ በሚገኙ የአማራ ተወላጆች ላይ የመዠንግር እና የሸኮ ተወላጆች አንድላይ በማበር የአርኛረኛ ተናጋሪዎችን እየጨፈጨፉ ሲሆን ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ በርካታ ሰዎች መሞታቸው ተሰማ።

(ከዚህ ቀደም ከጉራ ፈረዳ የተፈናቀሉ አማሮች፡ ፎቶ ፋይል)

(ከዚህ ቀደም ከጉራ ፈረዳ የተፈናቀሉ አማሮች፡ ፎቶ ፋይል)


ከአካባቢው የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው በስፍራው ይኖሩ የነበሩት እነዚሁ አማሮች ቤት ንብረታቸውን ለቀው ወደ አካባቢው ከተሞች እየተሰደዱ ሲሆን እስካሁንም እየተፈጸሙ ባሉ ጭፍጨፋዎች 25 ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።

በቤንች ማጂ ዞን በጉራፈርዳ ወረዳ እነዚህን ዜጎች የጨፈጨፉት የመዠንገርና የሸኮ ተወላጆች አዳዲስ የጦር መሳሪያዎችን መያዛቸውን የሚገልጹት የዘ-ሐበሻ የዜና ዘጋቢዎች ይህ መሳሪያ ለደቡብ ሱዳን ተብሎ የመጣ እንደሆነና ከጭፍጨፋው በስተጀርባ የመንግስት እጅ ሳይኖርበት እንደማይቀር የሚያሳይ ነው ሲሉ በአካባቢው ጥቃት የደረሰባቸውን አማሮች አስተያየት በመጥቀስ ዘግበዋል።

በጉራፈርዳ በተፈጠረው ጭፍጨፋ በአካባቢው ያሉ የመንግስት ወታደሮች ከመዠንገር እና ከሸኮ ተወላጆች ጋር መተባበራቸውን የሚገልጹት እነዚሁ የጥቃት ሰለባዎች ሆን ተብሎ የአማራን ሕዝብ ለማጥፋት እየተደረገ ያለ ሴራ ነው ይሉታል። በጉራፈርዳ መሬታችንን ለቃችሁ ውጡ በሚል እንዲህ ያለው ጭፍጨፋ ሲፈጸም የመጀመሪያው አለመሆኑ ይታወሳል።

በኢትዮ ምህዳር ላይ የተከፈተው ክስ ላይ አለመግባባት ተፈጠረ

$
0
0

‹ጋዜጣውንም ሆነ ጋዜጠኛውን አልከሰስኩም›› አቶ ማሙሸት አማረ

‹‹አቶ ማሙሸት የከሰሰበት ሰነድ በዝርዝር ተነቦልኛል›› ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ

MEADበኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ቅጽ ሁለት ቁጥር 80 ላይ የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ አበባው መሃሪ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ሊቀመንበሩ ‹‹ፖርቲውን እያፈረሱ ያሉት ምርጫ ቦርድ፣ ኢህአዴግና አቶ ማሙሸት አማረ በጋራ ሆነው ነው፡፡›› በሚል በሰነዘሩት ሀሳብ አቶ ማሙሸት አማረ ጋዜጣውን ከሰዋል በሚል የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ ማክሰኞ መስከረም 26/2007 ዓ.ም ማዕከላዊ ቀርቦ ቃል መስጠቱ ይታወሳል፡፡

ይሁንና አቶ ማሙሸት አማረ ጋዜጣውን አልከሰስኩም በማለት ዜናውን ያወጣውን የሰንደቅ ጋዜጣ ‹‹እንደ ጋዜጠኛ ግራና ቀኝ መረጃ ማየት ባለመቻላቸውና እኔንም ስላላናገሩኝ እንጅ እኔ አልከሰስኩም፡፡›› ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ አቶ ማሙሸት ጨምረውም ‹‹አራዳ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ፖሊስ፣ ማዕከላዊ ምርመራ ቃለ መጠይቁን የሰጡትን አቶ አበባው መሃሪን ለመክሰስ በበቀረብንበት ወቅት ጋዜጣውንስ ትከሳላችሁ? የሚል ጥያቄ ቀርቦልን የነበረ ቢሆንም ‹አንከስም፣ ይህ ጋዜጣውንም ሆነ ጋዜጠኛውን (ዋና አዘጋጁን) ሊያስከስሰው የሚችል ጉዳይ አይደለም፡፡ ስማችን ያጠፋው ቃለ መጠይቁን የሰጠው ሰው እንጅ ጋዜጣው ወይንም ጋዜጠኛው አይደለም› ብለን ጋዜጣውን ስለመክሰስ ቃል አልሰጠንም፣ መስካሪዎቹም ቃል አልሰጡም፡፡ ስለ አቶ አበባው እንጅ ስለ ኢትዮ ምህዳር ያወራነው ነገር የለም›› ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል የኢትዮ ምህዳር ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ ቃል ለመስጠት ወደ ማዕከላዊ ባቀናበት ወቅት አቶ ማሙሸት የከሰሱበት ሰነድ በዝርዝር እንደተነበበለት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ጋዜጠኛው አክሎም ‹‹ፖሊስ ሊከሰኝ ሰበብ ከፈለገ በአቶ ማሙሸት በኩል ሊመጣ አይችልም፡፡ አቶ ማሙሸት ነው ዱላ ያቀበላቸው፡፡›› ሲል ገልጾአል፡፡

ጋዜጠኛው ‹‹አቶ ማሙሸት ልክ ጋዜጣው እንደወጣ ስሜን አስጠፍተሃል በማለቱ እኔ የሰራሁት ቃለ መጠይቅ መሆኑንና ይህም ስም ማጥፋት እንዳልሆነ ከማስረዳትም በተጨማሪ፣ እሱንም ጓደኞቹንም ሀሳባቸውን ቢሰጡ እንደማስተናግድ ነግሬው ነበር፡፡ ነገር ግን እሱ እኔ ያለሁበት ቦታ መጥተህ ቃለ መጠይቅ ስራ በማለቱ የጋዜጠኝነት ሙያን የሚጋፋ በመሆኑ በጽሁፍ አሊያም መጥቶ ቃለመጠይቅ እንዲሰጥ ስጠይቀው ዝቶብኛል፡፡›› ሲል አቶ ማሙሸት ከመጀመሪያው ጋዜጣው ስማቸውን እንዳጠፋ እንደሚያምኑና ሊከሱ የሚችሉበትን መነሻ አብራርቷል፡፡

አቶ ማሙሸት በበኩላቸው ‹‹ሰንደቅ ሳያናግረኝ እኔ እንደከሰስኩት አድርጎ ዜና ሰርቷል፡፡ የኢትዮ ምህዳር ጋዜጠኛም አልደወለልኝም፡፡ ይህ ራሱ ሌላ ስም ማጥፋት ነው፡፡ መጀመሪያ እኛም መጠየቅ ነበረበት፡፡ ጋዜጠኛው መጀመሪያም ለእሱም የሰጠነው ሰነድ እጁ እያለ የአንድ ሰው ሀሳብ አቅርቧል፡፡ የእኛን ሀሳብ ለማቅረብ አልሞከረም፡፡›› ሲሉ ይወቅሳሉ፡፡ ጌታቸው በበኩሉ ‹‹አቶ አበባውን ባናገርኩበት ወቅት አቶ ማሙሸት ምንም አይነት ሰነድም መረጃም አልሰጠኝም፡፡ ሀሳቡን በነጻ ሀሳብም ሆነ በሌላ መልኩ መግለጽ እንደሚችል ግን ገልጨለት ነበር፡፡ አሁን አልከሰስኩም የሚለው የሚዲያ ጫና ሲበዛበት ነው፡፡›› ሲል ‹‹አልከሰስኩም›› የሚለው የአቶ ማሙሸት ማስተባበያ መሰረተ ቢስ መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

Source-  ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia

የእርቅና መግባባት ዳሰሳ ጥናት ውጤት (ዶ/ር ዘለዓለም እሸቴ ይመር)

$
0
0

የሚከተለው ውጤት ድህረ ገፆች ላይ ከወጡት ፅሁፎቼ ሊንክ በማድረግ በ www.myEthiopia.com ድህረ ገፅ ላይ የተሰበሰበ የዳሰሳ ጥናት ነው። ጥናቱ ሳይንሳዊ ያልሆነ ቢሆንም ለመንደርደሪያ ጥናትና አሳብ ሊረዳ ይችል ይሆናል ብዬ አስባለው። ይህ ማለት ስለ እርቅና መግባባት ውስብስብ ጥያቄ እልባት ለማግኘት አይደለም። ያ በእኔ አይሞከርም ከአቅሜ በላይ ነውና። ዓላማዬ ስለ እርቅ ቅድመ ሁኔታዎች መንደርደሪያ አሳብ ለመሰብሰብ በማሰብ ነው። እነሆ ድምፅ የሰጡትን ሰዎች አሳቦች አጠርና ጠቅለል አድርጌ ከዚህ በታች በጥሬው አቅርቤያለው። የራሴን ትንታኔ ትቸዋለሁ። ያንን ለአንባቢው እተዋለሁ። በዚህ ዳሰሳ ጥናት ላይ የተሳተፉትን ከልብ አመሰግናለው። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ። ፍቅርም ይስጠን። -—[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]——

survey1

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live