Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

በአፋር ክልል ለትምህርት ወደ ውጭ አገር ሊሄዱ የነበሩ ተማሪዎች ከጉዞ ታገዱ

0
0

አኩ ኢብን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው ወደ ተለያዩ የአውሮፓ ማለትም ወደ ስዊድን፣ ጀርመን፣ ቤልጂየም የመሳሰሉ አገራት ለትምህርት ሊሄዱ ተዘጋጅተው የነበሩ ተማሪዎች ባልጠበቁት ምክንያት እንዲቀሩ ታዘዋል።
news
የአፋር ክልልን እየመራ ያለው የአብዴፓ ፓርቲ እነዚህ ወጣት ምሁራን እንዳይሄዱ የከለከለበት ምክንያት «”ወደ አውሮፓ ከወጡ በዛው ይቀሩብኛል” የሚል ፍራቻ ሳይሆን አይቀርም» የሚሉ ብዙ አስተያየት ሰጭዎች አሉ። እነዚህ ተማሪዎችን ከትምህርት ያስቀሩት ወይም እንዳይሄዱ ያዘዙት የአብዴፓ ፓርቲ አባል የሆኑት የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አቶ አሚን አብዱልቃድር መሆናቸውም ተሰምቷል።

የሕወሓት አባላት የሆኑ ተማሪዎች በስኮላርሺፕ የትም ሃገር ለመሄድ እንደማይከለከሉ የማይከለከሉ ከመሆኑም በላይ የውጭ እድል እንደሚመቻችላቸው የሚገልጹ አስተያየት ሰጪዎች የአፋር ክልል ይህን ማድረጉ አስገርሟቸዋል። ይልቁንም በነዚህ ተማሪዎች ስም ሌሎች እንዳይሄዱበት ስጋት እንዳላቸው አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።


አቡነ ማቴዎስ ፓትርያርኩን ተቃወሙ፤ “አቡነ ጳውሎስ በአማካሪዎች ክፋት ዕድሜያቸውን አሳጥረዋል፤ ቅዱስነትዎም ያስቡበት”አሏቸው

0
0

ዋ/ሥራ አስኪያጅ አቡነ ማቴዎስ: ፓትርያርኩ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ከቅ/ሲኖዶሱ ያጡትን ይኹንታ በአቋራጭ ለማግኘት ‘በመልካም አስተዳደር’ ስም የጠሩትን ስብሰባ ተቃወሙ!

‹‹ባላወጣነውና ባላጸደቅነው ሕግ ማኅበራትን መፈረጅና ሕገ ወጥ ማለት አንችልም፡፡››
‹‹አቡነ ጳውሎስ በአማካሪዎች ክፋት ዕድሜያቸውን አሳጥረዋል፤ ቅዱስነትዎም ያስቡበት፡፡››
‹‹ከአለቆችና ጸሐፊዎች ጋራ የተደረገው ውይይት አባቶች የተዘለፉበትና ያዘኑበት ነው፡፡››
‹‹ለእገሌ ሚኒስትር እናገራለኹ፤ ለእገሌ ደኅንነት እደውላለኹ እያሉ አያስፈራሩን!!››
/ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ/

በአዲስ አበባ ታትሞ ዛሬ የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንደዘገበው

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ በፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ተጠርቶ መስከረም ፳፯ እና ፳፱ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. የተካሔደው ስብሰባ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱን ወቅታዊ ኹኔታ የማይገልጽ፣ መዋቅሩን ያልጠበቀ እና ጽ/ቤታቸው የማያውቀው መኾኑን በመግለጽ ተቃወሙ፡፡

የመ/ፓ/ጠቅ/ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ

የመ/ፓ/ጠቅ/ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ

‹‹የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደራዊ አስተሳሰብ ማበልጸግ›› በሚል ርእስ ከትላንት በስቲያ በመንበረ ፓትርያርኩ አዳራሽ የግማሽ ቀን ስብሰባ በተደረገበት ወቅት፣ የፓትርያርክ አቡነ ማትያስን የመግቢያ ንግግር ተከትለው ቅድሚያውን በመውሰድ የተናገሩት ዋና ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ÷ ‹‹አኹን ወደ ስብሰባው ስገባ ነው መልእክቱን የሰማኹት፤ አጀንዳውም ከመቅረቡ በፊት ከቋሚ ሲኖዶሱ ወይም ከእኔ ጋራ ምክክር አልተደረገበትም፤›› በማለት ስብሰባው መዋቅሩን ሳይጠብቅና ከዕውቅናቸው ውጭ የተጠራ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡

የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት አስተላልፎታል በተባለው የቃል ትእዛዝ መጠራቱ በተገለጸው በዚኹ ስብሰባ÷ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የመምሪያዎች ዋናና ምክትል ሓላፊዎች፣ የየመምሪያው ዋና ክፍሎች ሓላፊዎች፣ የድርጅቶች ዋናና ምክትል ሥራ አስኪያጆች፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአስተዳደር ሓላፊዎች፣ የዋና ክፍሎችና የክፍሎች ሓላፊዎች፣ የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቶች ዋናና ምክትል ሥራ አስኪያጆች መሳተፋቸው ተገልጧል፡፡
Mhbere Kidusan
በ፳፻፩ ዓ.ም. በቅ/ሲኖዶስ ውሳኔ በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የመልካም አስተዳደር እንቅስቃሴ መቀጣጠሉን ተከትሎ የቀድሞው ፓትርያርክ መዋቅሩን ሳይከተሉና ከቅ/ሲኖዶሱ ጋራ ሳይመክሩ ወስደዋቸው ነበር ያሏቸውን ርምጃዎች በመቃወም በወቅቱ የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳስ የነበሩት የአኹኑ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የሰጡት ቃለ ምልልስ በማስረጃነት ተይዞ እንደሚገኝ ያስታወሱት ዋና ሥራ አስኪያጁ፣ ‹‹ቅዱስነትዎ በምትካቸው ሲቀመጡ መዋቅሩን ሊጠብቁ ይገባል፤ መዋቅሩን ሳይከተሉና ከሚመለከተው አካል ጋራ ሳይመክሩ የሚሠሩት ሥራ ቤተ ክርስቲያኒቱን አደጋ ላይ የሚጥል ነው፤›› እንዳሏቸው ተመልክቷል፡፡

ዋና ሥራ አስኪያጁ ‹‹ውድቀት እንዳይደረስብዎ አማካሪዎችዎ ሊያዝንልዎ ይገባል፤›› ማለታቸውን የገለጹት የስብሰባው ተሳታፊዎች አያይዘውም ‹‹ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በአማካሪዎቻቸው ክፋት ከዕድሜያቸው ዐሥር ዓመት አሳጥረዋል፤ እርስዎም በአማካሪዎችዎ የተነሣ ዕድሜዎ እንዳያጥር ያስቡበት፤›› ሲሉ መምከራቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ውይይቱን በሰብሳቢነት የመሩት ፓትርያርኩ፤ ‹‹በሥራ ባለመታገዛቸውና ብቻቸውን በመኾናቸው›› ስብሰባውን ወደ ታች ወርደው ለመጥራት እንደተገደዱ አስረድተዋል፡፡ ፓትርያርኩ ባቀረቡት በጽሑፍ የተደገፈ ገለጻ÷ በቤተ ክህነቱ የመልካም አስተዳደር ዕጦቶች እንዳሉ፣ በሙሰኝነት፣ በዘረኝነትና በአድሏዊነት የሚገለጹ የብልሹ አሠራር ሒደቶች እንደሚታዩ ዘርዝረዋል፡፡

በቤተ ክርስቲያን ስም የሚደራጁ ማኅበራትና ግለሰቦች ሕግና ደንብ እየጣሱ መዋቅሯን እየተፈታተኗት እንዳለና ከመዋቅራዊ ቁጥጥር ውጭ የሚንቀሳቀስ ሀብትና ንብረት እያካበቱ በመኾኑ አካሔዳቸው ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን ጥንካሬና ህልውና ፍጹም አደጋ እንደኾነ አብራርተዋል፡፡ መልካም አስተዳደርን ከማስፈን አንጻር ኹሉም የሥራ ሓላፊዎች ራሳቸውን በመፈተሽና በማጽዳት ችግሩን በዘላቂነት ለማስወገድ በሚደረግ ጥረት የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፤ ያልተገባ ነው ያሉትን የማኅበራት አካሔድም ኹሉም ሊቃወመው ይገባል ብለዋል፡፡

ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ ይወቁባቸው ስላሉት የአማካሪዎቻቸው ጉዳይም ‹‹አማካሪዎቼ ዓላማዬን የሚጋሩና የሚያስፈጽሙልኝ ሰዎች ናቸው፤›› ያሉት አቡነ ማቲያስ ‹‹አኹንም የምቀጥልበት መኾኑን አሳውቃለኹ፤›› ብለዋል፡፡

‹‹የመልካም አስተዳደርን አስተሳሰብ ማበልጸግ›› በሚል ርእስ በፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ትእዛዝ በአ/አ ሀ/ስብከት የተጠራው ስብሰባ በርግጥም ስለ ርእሱ የተደረገ ሳይኾን በማኅበረ ቅዱሳንና በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ላይ ያነጣጠረ እንደነበር ቀንደኛው አማሳኝ ኃይሌ ኣብርሃ ቀድመው የተመረጡ ሰዎች ብቻ እንዲናገሩ በተፈቀደው ‘ውይይት’ ላይ ግልጽ አድርጓል፡፡ የስብሰባው እውነተኛ ዓላማ ደግሞ፣ ለሚመለከተው መንግሥታዊ አካል በይፋ ተነግሯል ከተባለው በተፃራሪ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ቅስቀሳ በማካሔድ ፓትርያርኩ በማኅበሩ ላይ የያዙት ውድቅ የተደረገ አቋም በቅዱስ ሲኖዶሱ ተቀባይነት እንዲያገኝ ጫና ለመፍጠር አልያም ለኃይል ርምጃ ለማመቻቸት የታቀደበት እንደነበር ‘ንቡረ እድ’ ኤልያስ ኣብርሃ በመንበረ ፓትርያርኩ በተካሔደው ስብሰባ ባራመደው አቋም ግልጽ አድርጓል፡፡ (ፎቶ: አ/አበባ ሀ/ስብከት)

‹‹የመልካም አስተዳደርን አስተሳሰብ ማበልጸግ›› በሚል ርእስ በፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ትእዛዝ በአ/አ ሀ/ስብከት የተጠራው ስብሰባ በርግጥም ስለ ርእሱ የተደረገ ሳይኾን በማኅበረ ቅዱሳንና በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ላይ ያነጣጠረ እንደነበር ቀንደኛው አማሳኝ ኃይሌ ኣብርሃ ቀድመው የተመረጡ ሰዎች ብቻ እንዲናገሩ በተፈቀደው ‘ውይይት’ ላይ ግልጽ አድርጓል፡፡ የስብሰባው እውነተኛ ዓላማ ደግሞ፣ ለሚመለከተው መንግሥታዊ አካል በይፋ ተነግሯል ከተባለው በተፃራሪ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ቅስቀሳ በማካሔድ ፓትርያርኩ በማኅበሩ ላይ የያዙት ውድቅ የተደረገ አቋም በቅዱስ ሲኖዶሱ ተቀባይነት እንዲያገኝ ጫና ለመፍጠር አልያም ለኃይል ርምጃ ለማመቻቸት የታቀደበት እንደነበር ‘ንቡረ እድ’ ኤልያስ ኣብርሃ በመንበረ ፓትርያርኩ በተካሔደው ስብሰባ ባራመደው አቋም ግልጽ አድርጓል፡፡ (ፎቶ: አ/አበባ ሀ/ስብከት)


[በስብሰባው የተሳተፉት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአስተዳደር ዋና ክፍል ሓላፊ፣ ‹‹አንድ ጣታችንን ወደሌላው ስንጠቁም ሦስቱ ወደ እኛ እንደሚያመለክት አንዘንጋ፤›› በማለት ፓትርያርኩ ስለ ሙስናና ብልሹ አሠራር፣ ስለ ጎጠኝነትና ብኩንነት፣ ፍትሕን ስለማጉደልና ንጹሑን ሰው ስለመበደል፣ ስለ ትጋት ማነስና አባቶችን ስለ መከፋፈል፣ ለምእመናን መልካም አርኣያ ስላለመኾንና ለሀገር አለመቆርቆር ሌሎችን ሲገሥጹና ሲኰንኑ ስለራሳቸውና ስለከበቧቸው አማካሪዎቻቸውም እንዲያስቡበት አስታውሰዋቸዋል፡፡]

‹‹ብቻዬን ነኝ፤ በሥራም አልታገዝኹም›› ለሚለው የፓትርያርኩ ወቀሳ ‹‹ቅዱስነትዎ አዝዘው ምን ያልተፈጸመ ነገር አለ?›› በሚል ምላሽ የሰጡት ዋና ሥራ አስኪያጁ፣ ‹‹ያልተፈጸመ ነገር ካለ ለጉባኤው በይፋ ይገለጽ›› ሲሉ ጠይቀዋቸዋል፡፡ የመልካም አስተዳደር ችግርና የችግሩ መገለጫዎች በርግጥም እንዳሉ ያልሸሸጉት ዋና ሥራ አስኪያጁ፣ መምሪያዎችና ድርጅቶች የበጀት ዓመቱን ዕቅድ በማውጣት፣ የክንውን ሪፖርት በአስተዳደር ጉባኤ በየወቅቱ እንዲያቀርቡ፣ ድክመቶች እንዲስተካከሉና ጠንካራ ጎኖች ታቅበው እንዲቀጥሉ መደረጉን በመግለጽ በፓትርያርኩ ጽሑፍ የቀረቡትን መረጃዎች ወቅታዊነት ሞግተዋል፡፡

በልማት ተግባራትና በሠራተኞች አያያዝ ባለፈው በጀት ዓመት የተፈጸሙ ተግባራትን የዘረዘሩት የጽ/ቤቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር አባ ኃይለ ማርያም መለሰ በበኩላቸው፤ በጥናት በተደገፉና ቀጣይነት ባላቸው የመልካም አስተዳደር ማሻሻያዎች የሚቀርቡ ቅሬታዎችና የተጉላሉ ባለጉዳዮች አለመኖራቸውን ገልጸዋል፡፡ ምክትል ሥራ አስኪያጁ አክለውም፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን የፋይናንስ ፖሊሲና የሒሳብ አያያዝ ሥርዐት ዘመናዊ ለማድረግ ዝግጅቱ መጠናቀቁን ጠቁመው ፓትርያርኩ በገለጻቸው የተጠቀሙባቸውን የችግር መግለጫዎችን አግባብነት እንደጠየቁ ታውቋል፡፡

መንግሥት የሲቪል ማኅበራትን የሚከታተለው ሕግ አውጥቶና ተቋም መሥርቶ መኾኑን፣ በሕጉ እገዛለኹ ያለ አብሮ እንደሚጓዝ፣ በሕጉ አልተዳደርም ያለ እንደሚወጣ የተናገሩት ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፣ ቤተ ክርስቲያን ግን መንፈሳውያን ማኅበራት የሚቋቋሙበት ሕግ እንዳላወጣችና የምታቅፍበት መዋቅር እንዳልዘረጋች ገልጸዋል፡፡ በአገልግሎት ላይ ያሉትን መንፈሳውያን ማኅበራት በሕገ ወጥነትና በመዋቅር ባለመታዘዝ ለመጠየቅና ለመፈረጅ ሕጉን አውጥቶ በሥራ ላይ ማዋሉ መቅድም እንዳለበት በማስገንዘብ የፓትርያርኩን ግምገማና አፈራረጅ እንደተገዳደሩት ተጠቅሷል፡፡

በተያያዘም የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ሓላፊና ከቀንደኛ አማሳኞች ኃይሌ ኣብርሃና ዘካርያስ ሐዲስ ጋራ በመኾን ስብሰባዎቹን ያስተባበረው የመዝባሪዎች አለቃ ኤልያስ ኣብርሃ፣ ‹‹ማኅበሩ ለሕግ የማይገዛና የማይታዘዝ ነው፤›› እያለ ስሙን ለይቶ ሳይጠራ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የሰነዘረው ውንጀላ የብዙኃኑን የስብሰባውን ተሳታፊዎች ተቀባይነት እንዳላገኘ ተመልክቷል፡፡

አቡነ ማቲያስ

አቡነ ማቲያስ


በኹኔታው የተበሳጨው የሚ/ር ሺፈራው ቤተኛ ኤልያስ ኣብርሃ፣ ‹‹እንዴት ሕገ ወጥ አይደለም ትላላችኹ? አክራሪነትና ጽንፈኝነት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አለ የሚባለው ከማኅበሩ ጋራ በተያያዘ ነው፤›› የሚል በእብሪትና ተንኰል የተሞላ ክሡ የስብሰባው የጋራ የአቋም መግለጫ ኾኖ እንዲወጣ አካሉ እስኪንዘፈዘፍ እየተወራጨ ያደረገው መፍጨርጨር በብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ የሰከነ ምከታና ማኅበሩ እንደ ቤተ ክርስቲያን ልጅነቱ በጥናት የታገዘ ምላሽ እንዲሰጠው በሚያሳስቡ የሥራ ባልደረቦቻቸው ጥረት እንዳልተሳካ ታውቋል፡፡]

በሌላ በኩል ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ፣ ‹‹ለኢትዮጵያ በረሓ ወርደው፣ ብረት አንሥተው የታገሉትና ዋጋ የከፈሉት ኹሉም ሕዝቦች ናቸው፤›› ብለው እንደተናገሩ የስብሰባው ተሳታፊዎች የጠቀሱ ሲኾን፣ ‹‹ሕገ መንግሥት ለኹሉም እኩል ነው፤ ለእገሌ ሚኒስትር እናገራለኹ፤ ለእገሌ ደኅንነት እደውላለኹ እያሉ አያስፈራሩን፤›› በማለት ፓትርያርኩን እንዳሳሰቧቸውም ሳይጠቅሱ አላለፉም፡፡

አቡነ ማትያስ በዚኹ ሳምንት ማክሰኞ፣ ከቋሚ ሲኖዶሱ ጋራ ሳይመክሩ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአድባራትና ገዳማት አለቆችና ጸሐፊዎች ጋራ ባደረጉት ስብሰባ፣ ማኅበረ ቅዱሳንን ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ጋራ ደርበው በሚወነጅሉ አንዳንድ አማሳኝ አስተዳዳሪዎችና ጸሐፊዎች ብፁዓን አባቶችን ማዘለፋቸውን የጠቀሱት አቡነ ማቴዎስ፣ በዚኽም ኹሉም አባቶች ቅሬታ እንደተሰማቸውና እንዳዘኑባቸው በግልጽ ነግረዋቸዋል፡፡

ፓትርያርኩ ዓመቱን በሙሉ በየደረጃው እቀጥልበታለኹ ባሉት ስብሰባ÷ አጀንዳዎች መዋቅር ሳይጠብቁ፣ ጥናት ሳይደረግባቸውና ሳይብላሉ ውይይቱ ለሚዲያዎች ዘገባ ክፍት መደረጉ ቤተ ክርስቲያኒቷን ለአላስፈላጊ የውጭ ተጽዕኖና ለአጉል ትችት እንደሚያጋልጣት በተሳታፊዎች አስተያየት ተተችቷል፡፡

”የመናፍቃኑ ተላላኪዎች መሠረተ ቢስ ውንጀላ ከአገልግሎታችን አንዲት ጋት ወደ ኋላ እንደማይመልሰን እንዲታወቅልን እንፈልጋለን” -ማኅበረ ቅዱሳን

0
0

“ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥ በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ…በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል ትን.ዕንባ.3፡17-19″ አትም ኢሜይል

በእግዚአብሔር ፈቃድ በቅዱስ ሲኖዶስ ይሁንታ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ለመደገፍና ለማጠናከር የተመሠረተው ማኅበረ ቅዱሳን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ አያሌ ፈተናዎችን እያሳለፈ 22 ዓመታት ተጉዟል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን በዓመታት ጉዞው ባከናወናቸው መልካም ተግባራት ታላላቅ የቤተክርስቲያን አባቶችን ጨምሮ እጅግ በርካታ ወዳጆችን እንዳፈራ ሁሉ ጥቂት በተቃራኒው የቆሙ ስሙን በየጊዜው በክፉ የሚያነሱ ቡድኖችም ተነሥተውበታል፡፡

ወዳጆቹ የቤተ ክርስቲያን ወዳጆች ናቸውና በአገልግሎቱ ተማርከው በሚሠራቸው መልካም ሥራዎች ተስበው ቤተ ክርስቲያን ያለባትን የአገልግሎት ክፍተት ለመሙላት በጋራ ከማኅበሩ ጋር በመሥራት ሲተባበሩ፤ በአንጻሩ ጠላቶቹ ደግሞ የተለያዩ አጋጣሚዎችን እያስታከኩ ማኅበሩን ለመወንጀል እየተጣጣሩ ይገኛሉ፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን እንዴት ወዳጆች አፈራ? ጠላቶችስ ለምን ተነሡበት?

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ፈቅዶ ከተመሠረተበት ጊዜ አንሥቶ ወጣቶችን በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከመደበኛው ትምህርታቸው ጎን ለጎን በየአካባቢው ወደሚገኙ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ሔደው መሠረታዊውን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት እንዲማሩ በማድረግ ሃይማኖታቸውን ጠንቅቀው እንዲያውቁና ቤተ ክርስቲያናቸውን እንዲጠብቁ እንዲሁም በዕውቀታቸው፣ በገንዘባቸውና በጉልበታቸው እንዲያገለግሉ በማድረግ፤ በተጨማሪም ወጣቱ ሀገሩንና ሕዝቦቿን አክባሪ፣ በሥነ ምግባር የታነጸ እንዲሆን በማስቻሉ ብዙ ወዳጆችን አግኝቷል፡፡

ከዚህም ሌላ የመናፍቃኑንና ቤተ ክርስቲያኒቱን እናድሳለን ብለው የተነሡትን የመናፍቃኑ ተላላኪ ቡድኖችን ሴራና የአክራሪ እስልምናውን እንቅስቃሴ በመረጃ አስደግፎ በማጋለጡ፣ ከክፉ ትምህርታቸው መመለስ ያልፈለጉ የተሐድሶ ቡድን አባላት ከቤተ ክርስቲያን እንዲወጡ ስለተወሰነባቸው እና ሌሎችንም የቤተ ክርስቲያኒቱን ችግሮች እየተከታተለ ለዕድገቷና ለብልጽግናዋ በመሥራቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የቤተ ክርስቲያን ወዳጆችን አፍርቷል፡፡

Mhbere Kidusanከዚህ በተቃራኒው የተሰለፉት ወገኖች ደግሞ ወጣቱን እንደጠፍ ከብት ወደ ማያውቀው የመናፍቃን አዳራሽ የመንዳት ልምዳቸው በመቋረጡና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በመግባት የሚያደርጉት ሥርዓቷን የማፋለስ እንቅስቃሴ፤ እንዲሁም አገልጋዮቿንና ምእመናኖቿን የማስኮብለሉ አካሔድ ማኅበሩ በክትትል በተለያዩ መረጃዎች ስለገለጠባቸው ማኅበረ ቅዱሳንን በጠላትነት በማየት ማኅበሩ እንዲፈርስ የማይቧጥጡት ዳገት የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፡፡

እነዚህ የቤተ ክርስቲያን የውስጥ ጠላቶች ለጥቂት ጊዜ ጋብ ብለው የነበሩ ቢሆንም አሁን ባገኙት አጋጣሚ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንጀራዋን እየበሉ የሚኖሩ ወዳጆቻቸውን በማጠናከርና በማስፋፋት በሚሊዮን የሚቆጠር በጀት ከወዳጆቻቸው ተመድቦላቸው የቤተ ክርስቲያኒቱን ሥርዓት ለማዛባትና በጎቿን ለመበታተን ሌት ከቀን እየሠሩ ነው፡፡

ይኼ ዕቅዳቸው የሚሳካው እንደ ማኅበረ ቅዱሳን ያሉ ለቤተ ክርስቲያኒቱ እምነትና ሥርዓት መጠበቅ የሚቆረቆሩ ማኅበራትን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ አጀንዳ በማድረግና እንዲበተኑ ክፉ ሥራ በመሥራት ነው፡፡ እነዚህ የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ይሔንን ከንቱ ቅዠታቸውን እውን ለማድረግም በቤተ ክርቲያኒቱ የተለያየ ሓላፊነት ላይ የሚገኙትን የዓላማቸው አስፈጻሚዎች ሁሉ እየተጠቀሙ እንደሚገኙም ይታወቃል፡፡

ከዚህም ሌላ ድብቅ ዓላማቸው እንዲሳካ ተላላኪዎቻቸው በቤተ ክርስቲያኒቱ ሥር የሚሆን ነገር ግን ስውር ዓላማ ያለው ማኅበር እንዲመሠርቱና ከዚህ በፊት ከንቱ ተግባራቸው ታውቆ በቤተ ክርስቲያኒቱ ታግደው የነበሩ ማኅበራት ሁሉ ከሞቱበት እንዲቀሰቀሱ እየሠሩም እያደረጉም ይገኛሉ፡፡

በቤተ ክርስቲያን ስም ድብቅ ዓላማቸውን ለማስፈጸም ያቋቋሟቸውና የሚያቋቁሟቸው፣ ማኅበራትንም ሕጋዊ ዕውቅና ለማሰጠት እንዲያመቻቸው ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከኔ ሌላ ሌሎች አያስፈልጉም የሚል አቋም ያለው ማኅበር እንደሆነ ያስወራሉ፡፡

በእርግጥ ማኅበረ ቅዱሳን በትክክል የቤተ ክርስቲያኒቱን ሥርዓትና ደንብ ተከትለው በሚቋቋሙት ማኅበራት ላይ የማኅበሩ ጠላቶች ከሚያወሩትና ከሚያስወሩት አሉባልታ የተለየ አቋም አለው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርቲያን የሁለት ሺሕ ዓመታት ታሪክ ያላት ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ትሁን እንጂ መንበሯ ከሊቀ ጵጵስና ደረጃ ወደ ፕትርክና ለማሳደግ አንድ ሺሕ ስድስት መቶ መራራ ዓመታትን አሳልፋለች፡፡ በዚህ ማለፏ ደግሞ ሌሎች አኀት አብያተ ክርስቲያናት የደረሱበት ዘመናዊ የአደረጃጀት ደረጃ ላይ ለመድረስ አልቻለችም፡፡ ልጆቿንም ጊዜው በሚጠይቀው መንገድ ለመምራት ሳትችል ስለቆየች እነዚህን ክፍተቶች የሚሞሉ አንድ አይደለም በርካታ ማኅበራት እንደሚያስፈልጓት ማኅበረ ቅዱሳን ያምናል፡፡ ነገር ግን እኩያኑ እንደሚሉት ሳይሆን እነዚህ ማኅበራት ሲቋቋሙ ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን ዕድገትና የአገልግሎት ሥምረት የሚንቀሳቀሱ ተልእኮአቸውና ዓላማቸው ተለይቶ የሚታወቅ፣ መንፈሳዊ ተግባርን ብቻ የሚፈጽሙ፣ የሚናበቡና በስልት ለአንድ ውጤት የሚተጉ ሊሆኑ ይገባቸዋል የሚል ጽኑ አቋም አለው፡፡

ይሔንን አቋሙን ደግሞ በርካቶች የሚደግፉት እንደሆነ ማኅበረ ቅዱሳን ያምናል፡፡ ምክንያቱም እነዚህ የመናፍቃኑ ተላላኪዎች በቤተ ክርስቲያን ስም ያቋቋሟቸው ማኅበራት ከዚህ በፊት በቤተ ክርስቲያን ላይ ጥለውት የሔዱት ጠባሳ የሚታወቅ ስለሆነ ማኅበረ ቅዱሳን በማኅበራት ላይ ግልጽ አቋም አለው፡፡ ከዚህም ሌላ እነዚህ የውስጥ ዐርበኞች ይኽ ስውር ዓላማቸው ያልታወቀባቸው ይመስል ማኅበሩን ለመወንጀል የማይለጥፉለት ታፔላ፣ የማይለፍፉት ወሬ የለም፡፡ ነገር ግን እነዚህ የቤተክርስቲያን ጠላቶች ስለማኅበሩ የሚያወሩት ሁሉ ከእውነት የራቀ እና ሁሉም የሚገነዘበው ግልጽ እውነታ መሆኑን ባለማወቃቸው እናዝናለን፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ምንም ስውር ዓላማ የለውም፤ ከማንኛውም የፖለቲካ አስተሳሰብ የጸዳና በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በተሰጠው መተዳደሪያ ደንብና መመሪያን ሳያዛንፍ እየሠራ ያለ፤ በተሰጠውም መተዳደሪያ ደንብና ሓላፊነት መሠረት ከአባላቱ የሰበሰበውን የገንዘብ መዋጮ ገቢና ወጪ እያሰላ በውስጥ ኦዲተሮችም እያስመረመረ በመሥራት ተጨባጭ ለውጥ ያመጣ ማኅበር እንጂ በወሬ የሚኖር አይደለም፡፡ ይሔንን አሠራሩንም ቀርቦ ማየት ይቻላል፡፡ አባላቱም በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው በጉልበታቸውና በመላ ሕይወታቸው ቤተ ክርስቲያንን የሚያገለግሉ እንጂ እንደ መናፍቃኑ ተላላኪዎች ለሆዳቸው ያደሩ፣ ሆዳቸው አምላካቸው የሆነባቸው እዚህም እዚያም ደሞዝ የሚቀበሉ አይደሉም፡፡

ማንኛውም አካል እንዲያውቅልን የምንፈልገው ሐቅ ማኅበረ ቅዱሳን ቅዱስ ሲኖዶስ ለሰጠው ሓላፊነትና አባላቱም ለገቡለት ቃል ኪዳን ሃይማኖታቸው የሚፈቅደውን መስዋዕትነት ለቤተ ክርስቲያን ልዕልናና ክብር ለመክፈል የተዘጋጁ እንጂ በተዛባ አመለካከት ወደ ኋላ የሚያፈገፍጉ አለመሆናቸውን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎቱ የሚታይ አሠራሩም ግልጽ ነው፡፡ ስለዚህም የመናፍቃኑ ተላላኪዎች መሠረተ ቢስ ውንጀላ ከአገልግሎታችን አንዲት ጋት ወደ ኋላ እንደማይመልሰን እንዲታወቅልን እንፈልጋለን፡፡ ርእይና ተልእኮአችንን ለማሳካት ዛሬም ነገም እንሠራለን፤ ትናንትን ያሻገረን እግዚአብሔር ዛሬንም ያሳልፈናልና፡፡
ይህ ጽሑፍ ግንቦት 16 ቀን 2003 ዓ.ም ወጥቶ የነበረና ታርሞ በድጋሚ የቀረበ ነው፡፡

የሰሞኑ የሥልጠና ፓለቲካ

0
0

የስምኦን ልጅ በረከት ከመክተብም አልፎ የሃገሪቷን ልሂቃን ኢንዶክትሪኔት እያደረገ ይገኛል። እስከማስታውሰው ድረስ የበረከት የመጨረሻ ህልም በዩንቨርስቲ ተጋባዥ መምህር ሆኖ ሌክቸር መስጠት ነበር። እነሆ!የልብን መሻት በማየት በላቀ ደረጃ የሚሰጠው ” ልማታዊ መንግሥት ” የሌክቸረሮች ሌክቸረር አደረገው። ርግጥ የድርጅቱ ከአጠገቡ አለመኖርም ህልሙን ያለጊዜው እንዲሳካ ሳያግዘው አልቀረም ። እኔ እምለው እሱ ባይኖር ኖሮ ማን ጵፎ ማን ያሰለጥን ነበር? አደራችሁን! ዶክተር ደብረጲዬን ብላችሁ የሀይሌን ልብ እንዳታቆሟት። የሀይሌ ልብ ከቆመ ሀገሪቷ በሁለት አመት ውስጥ ሁለት ጊዜ መስቀለኛ መንገድ ላይ ስለምትቆም ማናችንም አንፈቅድም ። ከሀይሌ ጋር ያላባራ ፀብ የገጠመው በረከትም ቢሆን!
ወደ ቁምነገሩ ልመለስ ።ወዳጄ ሰነዶቹን ሲልክልኝ ከተለመደው ውጭ አዲስ ነገር አይኖረውም በማለት ትኩረት አልሰጠሁትም ነበር። አላነበብኩትም ላለማለት ብቻ ስልኬን ከፈትኩ። ከሰነዶቹ ውስጥ ” የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ትግላችንና ፈተናዎቹ” የሚለው ቀልቤን ሳበው ። አንብቤ ስጨርስ ውስን ነጥቦችን መዝዤ በማውጣት ከትላንትናው አስተሳሰብ ጋር ማገናዘብ ጀመርኩ። እናም ስልኬን አውጥቼ የሚከተሉትን ቁምነገሮች ለመክተብ በቃሁ ፣
1• Paradigm Shift
bereket
ይህ ሰነድ ስርነቀል የአስተሳሰብ ለውጥ ያመጣው በስርአቱ አደጋ ላይ ነው። ድርጅቱ ከመሬት በታች ከመዋሉ በፊት በጳፉቸው ድርሳናትም ሆነ ገድሎች የስርአቱ አደጋ በዋነኛነት የሚመነጨው ከውስጥ ነበር። ቦናፓርቲዝም፣ ጥገኛ ዝቅጠት ፣ የመበስበስ አደጋ፣ እንደ አሣ ከጭንቅላቱ መሽተት ፣ ሙስና፣ ጠባብነት እና ትምክህት፣አድርባይነት… ወዘተ የውስጥ አደጋዎቹ መገለጫዎች ነበሩ።
ዛሬ የስምኦን ልጅ ምስጋና ይግባውና በዚህ ጉዳይ ላይ ስር ነቀል የአስተሳሰብ ለውጥ በማድረግ ( ” የአስተሳሰብ እድገት” አለማለቴን ልብ ይሏል) የስርአቱ አደጋ ከኢህአዴግ ውጭ እንደሚመነጭ ያበስራል። ለዚህ እማኝ እንዲሆን በገፅ 24 ላይ ፣
“… በስልጣን ላይ ሆኖ አገሪቷን የሚያምሰ የትምክህት ሀይል የለም። … በሥልጣን ላይ ሆኖ አገሪቷን የሚያተራምስ የጠባብነት ሐይል የለም።” በማለት ይገልጻል።
ለዚህ አስተሳሰብ ማጠናከሪያ የሚሆነው በዚሁ ገጵ ላይ ፣
“… ይህ መሰረታዊ ጉዳይ እንደተጠበቀ ሆኖ በሥልጣን ላይ ባለው ፓርቲና በመንግሥት መዋቅሮች የትምክህትና የጠባብነት አስተሳሰብን የሚያራምዱ ግለሰቦች አሉ።” በማለት ችግሩን በግለሰብ ደረጃ የሚገለፅ እንደሆነ ያሰምርበታል ።
ታዲያ የስርአቱ አደጋ የትነው ያለው?
2• ማነው ባለሳምንት?

የበረከት ማስታወሻ በኢህአዴግ ውስጥ ሰርጐ ገቦች መኖራቸውን አምኗል ። እነዚህ ሰርጐ ገቦች ከሌሎች ጋር በመቀናጀት ስርአቱ ላይ ፈተና እንደደቀኑበት በሚከተለው መልኩ በገፅ 24 ላይ ጠቅሶታል፣
“… ውጭ ሆነው ስርአቱን ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱ የትምክህትና ጠባብነት ሐይሎች ጋር በመቀናጀት ልዩ ልዪ ፈተናዎችን በመደቀን ላይ ይገኛሉ።”
ይህቺ አንቀጵ በንዴት እንደተጳፈች ታስታውቃለች። የንዴቱ ምንጭ የቅርብ ግዜውን የኦቦ አዲሱን እና የራሱን ቅሌት በማስታወስ የተጳፈች ትመስላለች ።
ኦቦ በንዴት ውስጥ ሆኖ፣
” … ሁለት ሶስተኛው መምህር የእኛ አባል ሆኖ በራሳችን ላይ ይሰለፉል” ነበር ያለው። የስምኦን ልጅ ደግሞ ቁርሴን ስበላ በሚል መንደርደሪያ የቅርብ ጓደኞቹ ሳይቀሩ ” ምርጫ የማይደርስ መስሎሀል?” በማለት እንደዛቱበት ተናግሯል ።
እናም አጨዳው ይቀጥላል ። ከበረከት ሰነድ ለመረዳት እንደሚቻለው ለመጠረግ የተዘጋጁት የአማራና ኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ የኢህአዴግ አባላት ናቸው።
ጠራጊው ማን ይሆን? ጠረጋው እስከየት ድረስ ይዘልቃል?

3• ትምክህት Vs አማራ
የበረከት ሰነድ በሚያስደነግጥ ሁኔታ ትምክህት ለአማራ ብሔረሰብ ተወላጆች ልዩ ስጦታ በማድረግ አቅርቧል። ሌላው ቀርቶ ከአማራ ክልል ውጭ በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ላይ የሚደርሰው ችግር ዋነኛ መንስኤ ” ከትግራይ የፈለቀው ገዥ መደብ እና ባለሟሎቹ” መሆኑን በመካድ በገፅ 29 ላይ፣
“… የዚህ አይነት ችግር ሲፈጠር በተጨባጭ የሚታወቁት መንስኤዎች ሁለት ናቸው ።አንዱ በራሳቸው የአማራ የተወሰኑ ወላጆች ዘንድ የሚታይ ችግር ሲሆን ፣ሌላው በሚኖርበት ህዝብ የተወሰነ ማህበረሰብ ዘንድ የሚታይ ችግር ወይም ድክመቶች ናቸው” በማለት ይገልጻል ።
አቶ በረከት ወክየዋለው የሚለውን የአማራ ብሔረሰብ በሌላ ክልል ሲኖር፣ የሚኖርበትን ብሄር ብሔረሰብ የሚንቅ፣የማያከብር፣ ማንነቱን የማይቀበልና የመጉዳት አዝማሚያ ያለው በማለት ይፈርጀዋል። ( የበረከትን ፅሁፍ ላለመዳችሁ አንባቢያን ” የተወሰኑ” ፣” ጥቂት”፣ ” እዚህ ግባ የማይባሉ”፣” እፉኚት” … ወዘተ የሚሉ የፊት ቅጥሎች (prefix) ካያችሁ እንደ ዳቦ ስም ውሰዷቸው)

4• ” የእኩልነት ጨዋታ ”
የበረከት ማስታወሻ በገፅ 34 ላይ ” የብሔር እኩልነት በተከበረበት የሌለ በማስመሰል።… በፌደራል ደረጃ እኩል የመሳተፍ መብት በተከበረበት በዚሁ አዲሱ ዘመን እነዚህ መብቶች እንደሌሉ ” በማለት የጠባብ ሐይሎች ተገቢ ያልሆነ ወቀሳ እንደሚያቀርቡ ያስገነዝባል። ይህን የአቶ በረከት መከራከሪያ እንደ ቅቡል ወስደን የሚከተለውን ጥያቄ እናንሳለት፣
* በፌደራል ደረጃ አራቱ ታዳጊ ክልሎች ዘወትር የውክልና ጥያቄ እንደሚያቀርቡ የዘወትር ሪፓርትህ ነው። እናም ስንት ሚኒስትር፣ ዴሬክተር፣ ስራ አስፈጳሚ… አለ? ( ከሀያ ሶስት አመት የሥልጣን ዘመን በኋላ የድሮውን መከራከሪያ እንዳታቀርብና እጄን በአፌ ላይ እንዳላገኘው።)
* አቶ በረከት ሠራዊቱን ለማመጣጠን እንደተቻለ በገፅ 31 ላይ አስታውቀሀል። ታዲያ ለምን የሐይማኖት ስብጥርን በአሃዝ አስደግፈህ እንዳቀረብከው የሰራዊቱን የአመራር ደረጃ በዛው መልኩ አቅርበህ አፉችንን አታዘጋንም?

5• አዲሳአባ

አቶ በረከት ያዘጋጀው ሰነድ ከአዲሳአባ ማስተር ፕላን ጋር ተያይዞ የነበረው ችግር ፣የሁከቱ ምክንያት እና መገለጫ የጠባብ ሐይሎች ዘመቻ እንደሆነ በገፅ 33 ላይ ያሳውቃል ። በርግጥ የኦህዴድ አመራር አባላትና የኦሮሚያ ሚዲያ ( ሳታቫኦ) እጃቸው አለበት ብሎናል። ከዚህ በተጨማሪም በዚሁ ገጵ ላይ፣
“… በአዲስ አበባ የፌደራል ዋና ከተማነትና በኦሮሚያ ክልላዊ ጥቅም መካከል ይህ ነው የሚባል ግጭት የለም” ይለናል ።
ጥያቄ አንድ: ማስተር ፕላኑ መጀመሪያ በተባለው መልኩ ሳይሸራረፍ ይፈፀማል ማለት ነው?
ጥያቄ ሁለት: የጥቅም ግጭቱ ከሌለ የኦሮሚያ ልዪ መብት እስከ አሁን ለምን አልተደነገገም?
ጥያቄ ሶስት: ችግር የፈጠሩት የኦህዴድ ባለሥልጣናት እነማን ናቸው? ( በነገራችን ላይ ኦቦ ጁነዲን ሳዶ አትላንታ ለሚገኙ ወዳጆቹ ” ያ! ማኪያቬሊ ሃገሪቷን የማትወጣበት አዘቅት ከቶ ሞተ ” እያለ እንደሚናገር ሰምተሀል መቼስ?)

6• ቤኔሻንጉል vs የደች በሽታ ( Dutch Disease)

አባይን መገደብ የማን አስተሳሰብ ነበር? የሚለው ጥያቄ ለጊዜው ይቆየንና ግድቡ እየተሠራበት ካለው ቦታ አንጳን አንድ ጥያቄ እናንሳ። በሕገመንግሥቱ የመገንጠል ጥያቄ ሊነሳ የሚችለው ከመከፉት( መበደል) ብቻ ሳይሆን ” የአይናችሁ ቀለም አላማረኝም፣ ብቻዬን መኖር ፈለኩ ” ከሚል ጫፍ የረገጠ ፈንጠዝያም ሊነሳ እንደሚችል ባለራእዪ መሪ ደጋግመው ነግረውናል። እናም ቤኔሻንጉሎች ” የመገንጠል ጥያቄ” ቢያነሱ ምላሻችን ምን ይሆናል?
( ምክር ቢጤ:የተሐድሶ ጊዜ ደጋግመን የዘመርናትን ” የደቾች በሽታ” በካሪኩለማችን ቢካተት ።)

7• የተዘነጋ ፍረጃ
ጓድ በረከት ለአማራ ህዝብ ትምክህት ፣ ለኦሮሞ ህዝብ ደግሞ ጠባብነት የሚባሉ ኢህአዴጋዊ ጥብቆ አጠለክ። የትግራይ ህዝብ የትኛውን ይልበስ?

ላ’ንዲት የገጠር ሴት – (በእውቀቱ ሥዩም )

0
0

Beweketu Seyoun joke about African leaders summit [Very Funny]

ስትፈጭ የኖረች ሴት፣
መጁ በመጠኗ፣ ወፍጮውም በልኳ ፣
ጓያ ትፈጫለች
ጓያ ሽሮ ሲሆን ያበቃል ታሪኳ።
አስባው አታውቅም..
ወደ ኦናው ምድር ለምን እንደመጣች፣
ከ’ለታት አንድ ቀን፣ከና’ቷ ሆድ ወጣች፣
ከ’ለታት አንድ ቀን፣ ጡት አጎጠጎጠች፣
ከ’ለታት አንድ ቀን፣ ለባሏ ተሰጠች።
ተዚያን ቀን ጀምራ፣
ተዚያን ቀን ጀምሮ፣
ድንግል ድንጋይ ወቅራ፣
ትፈጫለች ሽሮ።
አታውቅም፣
ማን እንደሚባሉ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣
አታውቅም፣
ሹማምንት በ’ሷ ስም፣ ምን እንደሚሠሩ፣
አነሳኹት ‘ንጂ፣ እኔም ለነገሩ፣
በፖለቲካ ጥበብ ራስን ማራቀቅ፣
ምን ይጠቅማትና ጓያዋን ለማድቀቅ።
ከቶ ማንም የለ, አበባ ‘ሚሰጣት፣
ከቶ ማንም የለ፣ ከተማ ‘ሚያወጣት፣
ከቶ ማንም የለ ፣ በዳንኪራ መላ፣ ወገቧን የሚያቅፋት፣
ልፋቷም፣ዕረፍቷም፣
ወደዚህ መጅ መሳብ
ወደዚያ መጅ መግፋት።
እንደ ዓባይ ፏፏቴ ፣ ሽሕ ዓመት ቢንጣለል፣
ቢጎርፍም ዱቄቱ፣
እንደ ሲኦል ወለል፣ ጫፍ የለውም ቋቱ።
ከዘመናት ባንዱ
መስተዋት ፊት ቆማ፣በተወለወለው፣
ፊቷን ለማዬት፣
ከጸጉራ ላይ ያለው
ዱቄት ይኹን ሽበት. ሲያቅታት መለዬት፣
ያኔ ይገባታል የተሰጣት ዕጣ፣
ከማድቀቅ ቀጥሎ፣መድቀቅ እንዲመጣ።
የመጅ አጋፋፏ-አምሳለ ሲሲፈስ፣
ከቋት ሥስት እንጅ፣ ሢሳይ አይታፈስ፣
ትቢያ ‘ሚተነብይ ዱቄት በዙሪያዋ፣
ከባርኔጣ አይሰፋም፣ የኑሮ ጣሪያዋ፣
‹‹ስትፈጭ የኖረች ሴት ›› ይህ ነው መጠሪያዋ።

በአፋር ክልል አሳዛኝ የጎርፍ አደጋ ደረሰ

0
0

አኩ ኢብን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው

በአፈር ክልል በአሚ ባራ ወረዳ በአዋሽ ሸለቆ ከተማና (በባዓዶህ አሞ ቀበሌ፣ በቦናት ቀበሌና በሓሶባ ቀበሌ ትናንት ከሌሊቱ ከ8:00 ሰዓት ጀምሮ ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ደርሷል። ጎርፉ ከጎረቤት ክልል የመጣ ሲሆን በዛ አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎችን ተፈናቅለዋል።

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)


በአሁን ሰአት ደግሞ ከሚባራ ወረዳ ዘግይቶ የደረሰን መረጃ እንሚያመለከተው እስካሁን በሰው ህይወት ላይ የደረሰ አደጋ ባይኖርም ነዋሪዎች ከቤታቸው ተፈናቀለው በትምህርት ቤቶች ይገኛሉ። በዛ አካባቢዎች የሚገኙ እርሻዎች ቤቶች እና ቁሳቁሶች ከጥቅም ውጭ ሆነዋል። ከክልልም ሆነ ከፌደራል መንግስት እስካሁን ለእነዚህ አደጋ ለደረሰባቸው ዜጎች የተደረገ እርዳታ የለም።

እስካሁን አማራጭ በማጣት በየትምህርት ቤቶች የገቡት እነዚህ ዜጎች በአደጋ ላይ ይገኛሉ።

“አሻራ”–በአንዳርጋቸው ጽጌ ዙሪያ ያጠነጠነች ልዩ ዕትም መጽሔት (PDF)

0
0

andargacew ashara magazine cover page
በአውስትራሊያ የሚገኙት ጋዜጠኞች አብይ አፈወርቅ እና ሳምሶን አስፋው በአንዳርጋቸው ጽጌ ዙሪያ ብቻ ያጠነጠነች አሻራ የተባለች የተለያዩ ታዋቂ ግለሰቦችን ቃለምልልስ እና ወቅታዊ ጽሑፍ የያዘች መጽሔት አሳትመዋል:: በኦን ላይን ለማንበብ የምትሹ እነሆ ተካፈሉዋት::

Click Here

የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ቀጠና ኃላፊ በደህንነት ሰዎች ተደበደቡ

0
0

ፍኖተ ነፃነት

10710933_711118828973054_6184937440487717547_nየአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የሰሜን ቀጠና ኃላፊ የሆኑት አቶ አዕምሮ አወቀ ሐሙስ ዕለት ከሥራ ወደ ቤታቸው ሲጓዙ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ለፍኖተ ነፃነት ገለጹ፡፡ እንደ አቶ አዕምሮ ገለፃ ይህ ድርጊት በየጊዜው እንደሚከሰትና በሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት እንቅስቃሴ በደሴ ከተማ በመኪና ለማፈን በተደረገው ግብግብ መኪና ውስጥ አስገብተው እንደተደበደቡ ራሳቸውን ለመከላከል በሚታገሉበት ወቅትም ጋቢና የተቀመጠውን ሹፌር መኪናውን ለማስነሳት ቁልፍ እንደያዘ እጁን ሲረግጡት በመጎዳቱ፣ ሁለቱ ከኋላ የያዟቸውን ደህንነቶች ለመከላከል ባደረጉት ግብ ግብ ስላየሉባቸው ገፍትረው ከመኪናው እንደጣሉዋቸውና ወደ አዲስ አበባ ከመጡም በኋላ ወንድማችንን ደብድበሃል የትም አታመልጥም በሚል ለገሃር አካባቢ በቡድን ድብደባ እንደፈጸሙባቸው ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ ከሰሜን የሚመጡ የፓርቲው አባሎችን ለመቀበል ዝግጅት በሚያደርጉበት ታህሳስ 17/2006 ዓ.ም ቤታቸው ባልታወቁ ሰዎች ተሰብሮ ንብረቱ በሙሉ ከቤት ተጭኖ ተወስዷል፡፡ ሐሙስ ዕለትም ከሥራ ወጥተው በትራንስፖርት ወደ ቤታቸው በሚሄዱበት ወቅት አየር ጤና አካባቢ ከአውቶቡስ ሲወርዱ ሁለት ደህንነቶች ግራና ቀኝ እጃቸውን በመያዝ እንዳይንቀሳቀሱ ካደረጉዋቸው በኋላ ሦስተኛው ደህንነት በድንጋይ ከጉልበታቸው በታች ደጋግሞ በመምታት ቀኝ እግራቸው ላይ ጉዳት አድርሰው ሦስቱም ከአካባቢው እንደተሰወሩ ገልጸዋል፡፡ ይህ ህገ ወጥ ድርጊት በሰላማዊ መንገድ ለውጥ እንዲመጣ መታገሌን እንዳቆም እንደማያደርገኝ ሊያውቁት ይገባል በማለት ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገልጸዋል፡፡


ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው በገዛ ፍቃዳቸው ለቀቁ –አቶ በላይ ፍቃዱ ቀጣዩ ፕሬዚዳንት በመሆን ተመረጡ

0
0

ፍኖተ ነፃነት

አንድነት ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው በገዛ ፍቃዳቸው ሥልጣናቸውን ለቀቁ
**********
አቶ በላይ ፍቃዱ ቀጣዩ ፕሬዚዳንት በመሆን ተመረጡ
*********

10171017_711922862225984_919845353769108652_nየአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ የተሰበሰበ ሲሆን በስብሰባውም ላይ በፕሬዚዳንቱ ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ከውስጥና ከውጭ በተፈጠሩ አንዳንድ የማያሰሩ ችግሮች፣ ካለባቸው የሥራ ጫና እና ፓርቲው ወደፊት አንድነቱን ጠብቆ ለ2007 ምርጫ አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ በማሰብ በራሳቸው ሙሉ ፍቃድ ከፕሬዚዳንትነታቸው በመልቀቅ ለብሔራዊ ም/ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት አሳውቀዋል፡፡
ብሔራዊ ም/ቤቱ የኢ/ር ግዛቸው የሰለጠነ ዲሞክራሲያዊ አካሄድ እጅግ ከፍተኛ በሆነ አክብሮት በመመልከትና በአገር ውስጥ በተቃውሞው ጎራ ለሚንቀሳቀሱና ለራሱ ለገዢው ፓርቲም ጭምር አስተማሪ የሆነ እርምጃ በመውሰዳቸው አክብሮትን ቸሯቸዋል፡፡
በቀጣይም የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ በሚፈቅደው መሰረት በፕሬዚዳንትነት የሚመሩ እጩዎችን በማቅረብ ለማስመረጥ አምስት አባላት በአስመራጭ ኮሚቴነት ተሰይመዋል፡፡

ራሳቸውን ለፕሬዚደንትነት በእጩነት ያቀረቡት

1ኛ. አቶ በላይ ፈቃዱ
2ኛ. አቶ ደረጀ ኃይሉ
3ኛ. አቶ ትዕግስቱ አወሉ ሲሆኑ እነዚህ እጩዎች ራሳቸውን ተራ በተራ ካስተዋወቁ በኋላ የብሔራዊ ም/ቤቱ አባላት በምስጢር ድምፅ አሰጣጥ ለሚፈልጉት ዕጩ ድምፅ ሰጥተዋል፡፡

በመጨረሻም በተደረገው የድምፅ ቆጠራ አቶ በላይ ፍቃዱ ከፍተኛ ድምፅ በማማምጣት አንድነት ፓርቲን በፕሬዚዳንትነት እንዲመሩ ተመርጠው ቃለ መሃላ ፈፅሟል፡፡
ስብሰባው እጅግ ዲሞክራሲያዊ በሆነ መግባባት ተጠናቋል ሲሉ የአንድነት ፓርቲ ሴክሬታሪያት ለፍኖተ ነፃነት ገልጸዋል፡፡

10710923_711918948893042_1548699492155811471_n

10171017_711922862225984_919845353769108652_n

10711112_711918818893055_3812820930564355730_n

 

10710635_711919072226363_136347616544957757_n 1779957_711919258893011_2902929528752558287_n

ባለሃብቱ የተከራካሪያቸውን ጠበቃ ገድለው ተሰወሩ

0
0

tebekaw
-ከጠበቃው ጋር የተመቱት ረዳት ጠበቃ ተርፈዋል

-ተጠርጣሪው ባለሀብት አለመያዛቸውን ፖሊስ ገልጿል

በደቡብ ክልል ሐዋሳ ከተማ መስከረም 27 ቀን 2007 ዓ.ም. የብሉ ናይል ሆቴል ባለቤት ናቸው የተባሉ ባለሀብት፣ በፍትሐ ብሔር ክስ ይሟገቷቸው የነበሩ ጠበቃ በሽጉጥ መትተው መግደላቸውንና ረዳታቸውን ማቁሰላቸውን ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

የሆቴሉ ባለቤት የተከሰሱበት የፍትሐ ብሔር ጉዳይ ለጊዜው ባይታወቅም፣ እሳቸውን ወክለው ከሚከራከሩት ጠበቃ በተቃራኒ ሆነው ሲከራከሩ የነበሩት ጠበቃ ዳንኤል ዋለልኝ፣ በጥይት ተመትተው እንደወደቁ ወደ ሆስፒታል ቢወሰዱም ሊተርፉ አለመቻላቸውን ምንጮች አስረድተዋል፡፡

አንገታቸው አካባቢ ተመትተው የነበሩትና የአቶ ዳንኤል ረዳት መሆናቸው የተገለጸው አቶ ዳግማዊ አሰፋ፣ አዲስ አበባ ኮሪያ ሆስፒታል መስከረም 27 ቀን 2007 ዓ.ም. ማምሻውን ገብተው በተደረገላቸው የቀዶ ሕክምና መትረፋቸውንም ምንጮች አክለዋል፡፡

ባለሀብቱ በሟቹ ጠበቃ በሌላም ክርክር መሸነፋቸውንና አሁንም በመከራከር ላይ ባሉት የፍትሐ ብሔር ክርክር በመሸነፍ ላይ በመሆናቸው ምክንያት ዕርምጃውን ሳይወስዱ እንዳልቀሩ የሚናገሩት ምንጮች፣ ጠበቃ ዳንኤልንና ረዳታቸውን በጥይት የመቷቸው በቢሮአቸው በሥራ ላይ እንዳሉ ከጠዋቱ አራት ሰዓት አካባቢ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የደቡብ ክልል ፖሊስ ስለ ጉዳዩ ከሪፖርተር ለቀረበለት ጥያቄ በሰጠው ምላሽ፣ ድርጊቱ እውነት መሆኑ አረጋግጦ ተጠርጣሪው ግን አለመያዛቸውን አስታውቋል፡፡ ፖሊስ በክትትል ላይ መሆኑና ተጠርጣሪው ከአገር እንዳልወጡም አክሏል፡፡

የሟች ጠበቃ ዳንኤል ዋለልኝ አሰፋ የቀብር ሥነ ሥርዓት በሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን መስከረም 29 ቀን 2007 ዓ.ም. መፈጸሙንም አስታውቋል፡፡

የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በሕግ ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ማግኘታቸውንና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በሰብዓዊ መብት አያያዝ ከዩኒቨርሲቲ ኦፍ ሳውዝ አፍሪካ በዚህ ወር ያገኙ እንደነበር የቅርብ ጓደኞቻቸው ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የአቶ ዳንኤልን ቤተሰቦችም ሆነ የተጠርጣሪውን ቤተሰቦች ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡

ምንጭ፡ ሪፖርተር ጋዜጣ

መኢአድ ታላቅ የተቃዉሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ሊያደርግ ነው

0
0

ለተቃውሞ ሰልፉ ህዝቡ እንዲዘጋጅ ጥሪውን አቅርቧል።

aeupበነገው ቀን ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት የተቃውሞ ሰልፉን ቀን ይፋ ያደርጋል ተብሎ የሚጠበቀው መኢአድ በፋሽሽቱ ወያኔ በጋምቤላ በጉራፈርዳ እና በሱማሌ ክልል እየተካሄደ ያለዉን የዘር ማጥፋት ወንጀል በጋራ ለማስቆም መላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚሳተፍበት ተከታታይ የተቃዉሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ይደረጋል ሲል የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ አስታወቀ።

“በዉጭም በሃገር ዉስጥም የምትገኙ ኢትዮጵያዊያን ከጎናችን በመቆም ይህን ዘረኛ ስርዓት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ በዲሞክራሳዊ ስርዓት እንቀይረዉ” ያለው መኢአድ አስፈላጊዉን ዝግጅት ሁሉ ማጠናቀቁን ገልጾ ለተቃውሞ ሰልፉ ህዝቡ እንዲዘጋጅ ጥሪውን አቅርቧል።

በግልጽ እንነጋገር – (ይሉኝታ፣ ምሁራን፣ ትግልና ሀገር በኢትዮጵያ)

0
0

አንዱ ዓለም ተፈራ

የእስከመቼ አዘጋጅ

ጥቅምት ፫ ቀን ፳ ፻ ፯ ዓመተ ምህረት ( 10/13/2014 )

eskemecheበአሁኑ ሰዓት በሀገራችን በኢትዮጵያ ያለውን ተጨባጭ የፖለቲካ ሁኔታ የማያውቅ ኢትዮጵያዊ የለም። ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ ሁላችንም አንድ ስምምነት ላይ ነን። በአንድነት ያልተገኘንበት፤ ምን ይደረግ? በሚለው መፍትሔ መሥጠቱ ላይ ነው። መፍትሔ ደግሞ ከመቅረቡ በፊት፤ ካለው ተጨባጭ ሁኔታ አልፎ፤ በግንዛቤያችን ደረጃ ያለንበትን መመርመሩ ግዴታ ይሆናል። እንግዲህ የዚህ ጽሑፍ ማጠንጠኛ ይኼው የግንዛቤያችን ጉዳይ ነው። በትግሉ ዙሪያ፤ ድርጅቶች፣ ምሁራን፣ ግለሰቦች ሞልተናል። እያንዳንዳችን የምንፈልገውን እናውቃለን። የሚያስማማን ደግሞ እያንዳንዳችን ከምንፈልገው መካከል ያለው የጋራ ፍላጎታችን ነው። ይህ የየግል ፍላጎታችን በሀገር ደረጃ ሲቀመጥና የጋራ የሆኑት ከመካከሉ ተጎልጉለው ሲወጡ፤  ሀገራዊ መታገያ ዕሴቶቻችን ነጥረው ብቅ ይላሉ። በዚህ ጽሑፍ፤ የሀገራችን፣ የትግላችን፣ የምሁራን ሚናና የይሉኝታችንን አስተዋፅዖ አጤናለሁ። እነኚህ፤ በያዝነው ትግል ያላቸውን ድርሻ ተንትነን ስንረዳ፤ ውጤታማ ወደ ሆነ መንገድ እናቀናለን።

በይሉኝታ ትግል አይካሄድም። ትግሉ የደረሰበትን ደረጃ መርምረን፤ ግስጋሴውን በማጥናት፤ በጎውን በመመዘገብና ችግሩን በመለየት እርማት አድርገን፤ መንገዱን የማቅናት ግዴታ አለብን። በየጓዳችን የምንናገረውና በአደባባይ የምናቀነቅነው አንድ ካልሆነ፤ አስመሳዮች ነን። በየጓዳችን፤ “አንድነት እኮ አንደያ ነው።” “መኢአድንማ ተወው።” “ግንቦት ሰባት እኮ እንዲህ ነው።” “ኢሕአፓ እኮ እንዲያ ነው።” “የሽግግር መንግሥት ባዮች ደሞ እንደዚህ ናቸው።” “የምን ሸንጎ አመጣህብኝ! ለመሆኑ እነሱ ማናቸው?” “የሚረባ ምን ድርጅት አለ ብለሽ ነው?” “አርፎ መቀመጥ ይሻላል።” “ሁሉም አይረቡም።” እያልን በአደባባይ ደግሞ፤ “ወያኔ ዛሬ ይወድቃል።” “ነገ ሕዝቡ ያቸንፋል።” “መተባበር አለብን።” “ሰላማዊ ሰልፍ እንውጣ!” “ለኦባማ ደብዳቤ እንጻፍ።” “ሀገሬን እወዳለሁ።” ብንል፤ ሌሎችን ሳይሆን ራሳችንን ነው ማታለል የያዝነው። ወይ አንድ ጊዜ ቅርጦ ከወያኔ መላተምና ለሆድ ማደር! አለያ ደግሞ፤ በቅጡ ሰፈር ለይቶ ከሕዝብ መወገን ነው። ይሉኝታ ቀን አይገፋም፤ አፍ ብቻ ነው የሚያለፋው። ራስን ብቻ ነው የሚያስገምተው። ድርጅት አለኝ ብሎ መንደላቀቅ፣ እየታገልኩ ነው ብሎ መኩራራት፣ ያለኔ ሁሉም አይሆንም ብሎ ማቅራራት፣ ታሪክ አለኝ ብሎ መደንፋት የትም አያደርስም። ለሕዝባዊ ትግሉ ጠብታ እንኳን አይረዳም። በግልጽ መነጋገሩና እውነተኛውን መንገድ መከተሉ ብቻ ነው የሚያዋጣው። በያንዳንዱ ድርጅት ጉድለት አለ። አዎ ጉድለት አለ። ባሁኗ ሰዓት መቶ በመቶ ትክክለኛ የሚባል ድርጅት የለም። እያንዳንዱ ድርጅት ደግሞ ጥሩ የሆነ ጎን አለው። ከያዝናቸው ሌላ ከሰማይ የሚመጣ የለም። ያሉትን በቀና መመርመርና አስተካክለን ወደፊት መጓዝ አለብን።ታዲያ ጥሩውን አጉልቶ፤ ለጎደለው ማስተካከያ አበጅቶ፤ አነፃጽሮ ቢያወጡት፤ ሁሉም ድርጅቶች አንድ ይሆናሉ።

ይህን ግልጽ ላድርገው። ሁሉም ድርጅቶች፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት መሆኑን ያውቃሉ። በሀገራችን ያለው መንግሥት፤ ፀረ-ኢትዮጵያ መሆኑን ይቀበላሉ። መወገድ እንዳለበት ያምናሉ። ሕዝቡ መብቱን አስከብሮ፤ የራሱን ምርጫ በትክክለኛ መንገድ በቦታው መተካት እንዳለበት ይቀበላሉ። እንግዲህ እነዚህ መሠረታዊ የሆኑ የጋራ የትግል ዕሴቶቻችን ናቸው። ዴሞክራሲያዊ አሠራርና የሕግ የበላይነት በሀገራችን እንዲሰፍን ሁሉም ይፈልጋሉ። ይህም በጣም ጠቃሚ ዕሴት ነው። በተጨማሪ፤ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ተሳትፎ መደረግ ያለበት፤ በኢትዮጵያዊ ዜግነት ላይ የተመሠረተ፤ እያንዳንዷ ኢትዮጵያዊትና እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በግለሰብ፤ የዴሞራሲያዊ መብቶች ተከብረውላቸው፤ በኢትዮጵያዊነታቸው ብቻ መሆን እንዳለበት ያምናሉ። ይህ እንግዲህ መታገያና የምንታገልለት ጉዳይ ነው። ታዲያ ለዚህ ነው ሁሉም ድርጅቶች አንድ ይሆናሉ ያልኩት። ይህን የማይቀበል ድርጅት ካለ፤ ፈርተን ወይንም በይሉኝታ፤ ሕልውናው እንዲቀጥል መንገድ መጥረግ የለብንም። ይህ ይሉኝታ ሳይሆን ልበ ቢስነትና ተልፈስፋሽነት ነው። ትግሉ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት መክፈል ቢያቅተን፤ ቢያንስ እውነቱን ተናግረን ራሳችንን ነፃ ማሳደር አይኖርብንም? ትግል እኮ፤ ራሳችንን ለሌሎች ሕልውና አሳልፈን መሥጠት ማለት ነው። የዚህ ሀ ሁ ደግሞ መጀመሪያ ለምናምንበት መቆም ነው። ወደ ምሁራን!

በያዝነው ትግል፤ ምሁራን ከፍተኛ ሚና አላቸው። በኛ ሀገር ባሁኑ ሰዓት ምሁራን በያሉበት፤ ግዴታቸውን፤ ማለትም ታሪካዊ ተግባራቸውን እያከናወኑ አይደሉም። ታሪካዊ ግዴታቸውን ለመወጣት፤ የአንድ ድርጅት አባል መሆን ወይንም አለመሆን መለኪያው አይደለም። ትግሉንና ሂደቱን መርምሮ፤ ትክክለኛ መፍትሔ ብሎ የሚያምንበትን በግልጽ ለሕዝቡ በማቅረብ፤ ድርጅቶችም ሆኑ ግለሰቦች ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲያገኙ ማድረግ የምሁራኑ ተግባር ነው። ትግሉን ከመመርመር ይልቅ ላሉበት ድርጅት ተገዥ በመሆን፤ ሁሉንም ጉዳይ በድርጅቶቻቸው ዓይን የሚመለከቱ ከሆነ፤ ምሁር የሚያስብላቸውን መለኪያ አያሟሉም። አስተዋፅዖም የላቸውም። የድርጅታቸው እንጂ የሀገራዊ ጉዳዩ መልስ ሠጪ ባለመሆናቸው፤ ትግሉን እየጎዱ ነው። ለአንድ ምሁር፤ ሀገራዊ ተጨባጭ ሁኔታውን መዝኖ መፍትሔ ማቅረቡ፤ ከፖለቲካ ድርጅት አባልነቱ ጋር የተያያዘ አይደለም። መሆንም የለበትም። ይህ ለተጨባጩ ሁኔታ የሚሠጥ ተጨባጭ መልስ ነው። በአቀራረብና በቅደም ተከተል፣ በዘዴና በስልት፣ ወይንም ትግሉ ሊወስድ በሚችለው አቅጣጫና የሂደቱ ፍጥነት ላይ የተለያየ አመለካከት ይኖራል። ይህ በርዕዩተ ዓለምና ውጤቱን ከማፋጠን ወይንም ጉዳቱን ከመቀነስ ድርጅታዊ መልክ ይይዛል። ይሁን። ያኔ ምሁራን ጎራ ሊለዩ ይችላሉ። መሠረታዊ በሆነው ተጨባጭ የሀገራችን የፖለቲካ ሀቅና አጠቃላይ መፍትሔው ላይ ግን ልዩነት ሊኖር አይገባም። ተጨባጩ የፖለቲካ ሀቅ አንድ ነው። ከመልሶቹ ሁሉ ደግሞ ትክክለኛው አንድ ነው። ወደዚያ ለመድረስ በሚወስደው መንገድ መለያየት ይቻላል። ምሁራን በተጨባጩ ሀቅና በትክክለኛው መልስ አይለያዩም። ታዲያ ይኼን የኛ ምሁራን አልተገበሩትም።

የምሁራን ትኩረት መሆን ያለበት፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባርን ተግባር መዘርዘርና ማውገዝ ሳይሆን፤ ወደፊት የሚያሳይ መፍትሔውን በመጠቆም፤ ምን መደረግ እንዳለብት ማሳየት ነው። እናም ለምን መተባበር አቃተን? ለምን ትግሉ ባለበት ይረግጣል? ድርጅቶች ትግሉን እየጠቀሙ ነው ወይንስ እየጎዱ? አደረጃጀታቸው ለያዝነው ትግል እየረዳ ነው ወይንስ እየጎዳ? ለምን የታጋዩ ጎራ ባንድነት አልተሰለፈም? ለአለመሰባሰባቸው አደረጃጀታቸው አስተዋፅዖ አያደረገ ነው ወይንስ አይደለም? የመታገያ ዕሴቶቻችን ምንድን ናቸው? ድርጅቶች ይሰባሰቡ ስንል በምን ዙሪያ ነው? መሰባሰቢያ ማዕከላዊ ጉዳይ ከሌላቸው ለምን ይሰባሰባሉ? ሀገራዊ ራዕያችን ምንድን ነው? የሚለውን፤ በየድርጅቶቹ መርኀ-ግብር ከሠፈረው ግባቸው በስተቀር፤ ሀገራዊ የሆነ መልስ የሠጡ ምሁራን አልተገኙበትም። እናም ምሁራን በምሁርነታቸው በቦታቸው አልተገኙም። አንድም ፈሪዎች በመሆንና በመደበቅ አንገታቸውን ደፍተዋል፣ ሌላም ለድርጅቶቻቸው አሽከር በመሆን በድርጅቶቻቸው መነፅር ብቻ ተመልካች ሆነዋል? አለያም ሌሎች ይሥሩት በማለት በየግል አጀንዳቸው ተጠምደዋል። ይህ ምሁራዊነት አይደለም። ምሁር ማለት፤ ጨለማውን ገልጦ የሚያጠራ፣ ያልተረገጠውን ዳስሶ የሚያሳይ፣ ያልተዳሰሰውን ደፍሮ የሚቃኝ፣ ማለት ነው። እናም ምሁራን በምሁርነታቸው በቦታቸው አልተገኙም።

ትግሉ የኛ እንጂ የመጪዎቹ ወይንም የሌሎች አይደለም። አንድነት ግዴታ ነው። ማድረግ ያለብንን እና የኛ የሆነውን ኃላፊነት፤ ለማንም ልናስተላልፈው አይገባም። ይህ በኛ ወቅት ያለና የኛ ሀገራዊ ግዴታ ነው። ሀገራችን አሁን ላለችበት የፖለቲካ ሁኔታ የትናንትኖችን መውቀስ ወይንም ለነገዎቹ ማስተላለፉ ተገቢ አይደለም። ይህ የራሳችን የአሁኑ ኢትዮጵያዊያን ኃላፊነት ነው። የያዝነውን ትግል በሚመለከት፤ ባሁኑ ሰዓት የታጋዩ ወገን አንድ ማዕከል የለውም። ባሁኑ ሰዓት የተጋዩ ወገን አንድነት የለውም። ባሁኑ ሰዓት የተጋዩ ወገን ትግሉን በትክክል አልተነተነውም። ባሁኑ ሰዓት የታጋዩ ወገን የአንድነት ሀገራዊ ራዕይ የለውም። ባሁኑ ሰዓት የተጋዩ ወገን በትክክል አልተደራጀም። ባሁኑ ሰዓት የተጋዩ ወገን በትክክል ትግሉን አልመራም፤ እየመራም አይደለም። ስለዚህ የኢትዮጵያ ሕዝብ፤ የታጋዩን ወገን፤ ከትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር የተሻለ ብሎ እንዳማራጭ እንዲወሰደው አስተማማኝ ሆኖ አልተገኘም። በርግጥ በማይካድ ደረጃ ሀገር ቤት ውስጥ ወደፊት የመንቀሳቀስ ሂደት ይታያል። አጥጋቢ አይደለም። ነገር ግን አጥጋቢ ባይሆንም፤ ያለው አማራጭ ያ ብቻ ሆኗል። ከዚያ የተሻለ ማድረግ እንችላለን። ትግሉ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ምርጫ ሆኖ የቀረበ አይደለም። በመኖርና ባለመኖር መካከል ግብግብ ሆኖ ስለተጫነው ብቻ ነው። እናም በማንም ውዴታ ወይንም ፍላጎት የተመሠረተ አይደለም። እኛ አስተዋፅዖ ለማድረግ ከፈለግን፤ የምንችለው፤ ጠንካራ የሆነ “የኢትዮጵያዊያን የነፃነት ንቅናቄ” ማካሄድ ነው። ለዚህ ንቅናቄ ደግሞ መሠረታዊ የትግሉ ዕሴቶቻችን ከላይ የተጠቀሱት ናቸው። እኒህም፤

ሀ) የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነትና ሉዓላዊነት መረጋገጥ፤

ለ) የኢትዮጵያ አንድ ሀገርነትና አንድ ብሔርነት መጠበቅ፤

ሐ) የሕግ የበላይነት በኢትዮጵያ መስፈን፤

መ) የያንዳንዷ ኢትዮጵያዊትና የያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር፤ ናቸው።

ከዚህ በላይ የተዘረዘሩት ሁሉን የኢትዮጵያዊያንን ፍላጎትና አሁን ያሉትን ድርጅቶች በሙሉ ፍላጎት የሚያሟሉ የትግል ዕሴቶች ናቸው። በነዚህ ዙሪያ የሚደረገው ትግል፤ አስተማማኝ የሆነ የወደፊት እንዲኖረን ይረዳናል። በርግጥ አመራሩን የሚሠጡት ግለሰቦች ወሳኝነት አላቸው። በዙሪያቸው የሚኮለኮሉትም ወሳኝነት አላቸው። አቤት ወዴት ብሎ፤ ሎሌ ይመስል አብሮ የሚነጉድ ተከታይ አሽከር ነው፤ እንጂ የድርጅት አባል አይደለም። ዴሞክራሲያዊ አሠራር ባልዳበረበትና ለሕግ መገዛት ባልጠነከረበት ትግላችን ውስጥ፤ ግለሰቦች የሚጫወቱት ሚና ከባድ ነው። ይመለካሉ። እስኪ ተመልከቱ፤ በየድርጅቶቹ ውስጥ ያሉ መሪዎች፤ እንደግል ንብረታቸው፤ ድርጅታቸው ከተመሠረተ ዕለት ጀምሮ ብቻቸውን ሲያዙበት አንዳንዶቹ አስርታት አመታት፤ ሌሎቹ ደግሞ ድርጅታቸው ከተፈጠረ ጀምሮ ያለውን ዕድሜ አስቆጥረዋል። አንድም ተከፋፍለው፣ አለያም ተገደው ካልሆነ በቀር ለውጥ የለም። መወራረስና ወጣቶቹን ወደፊት ማምጣት ትልቁ ነውር ነው። ስም የማልጠቅሰው፤ ያልተጠቀሰ ይኖርና እኔ የለሁበትም እንዳይል፤ ሁሉም በሙሉ በዚህ የተዘፈቁ ስለሆነ ነው።

ለግለሰቦች ያለኝ መልዕክት፤ ትክክለኛ የሆነ ኢትዮጵያዊ መንግሥት በሀገራችን እንዲኖር ሁላችን እንፈልጋለን። በምንችለው ደግሞ እየጣርን ነው። በየጊዜው መስዋዕት እየተከፈለ ነው። ትግል የበኩሌን እስካደረግሁ ድረስ ሌላ ኃላፊነት የለብኝም ብለን የምንቀመጥበት ክስተት አይደለም። ትግል የኛን ጠንካራ አስተዋፅዖ ከሌሎች ጠንካራ አስተዋፅዖ ጋር በመደመር፤ ካለንበት ወደፊት የሚኬድበት ነው። ባለንበት ከረገጥን፤ መመርመር ያለብን ጉዳይ አለ ማለት ነው። አንድም ትክክለኛ ያልሆነ የትግል ግብ ነድፈናል አለያም ትግሉ ለሚጠይቀው ትክክለኛ ድርጅት ይዘን አልተገኘንም ማለት ነው። ይኼ መመርመር አለበት። እንዲህ ካላደረግን፤ እንዲያው የምናደርገውን የማናውቅ ነን ማለት ነው።

በታጋይ ድርጅቶቹ መሪዎች በኩል ለድርጅቶች ያለኝ መልዕክት፤ ስትታገሉበት ላለው መርኀ-ግብር፤ እስከዛሬ በአባላት ከፍተኛ መስዋዕትነት፤ የምትችሉትን እያደረጋችሁ ትግሉን አቆይታችሁታል። ከልባችሁ የሀገራችንን ነፃ መውጣት ፈልጋችሁ ጥራችኋል። በቂ ሆኖ አልተገኘም። እናም አንድም ትግሉን፤ አለያም አደረጃጀታችንን በጥያቄ ውስጥ ያስገባ ሀቅ በላያችን ላይ መጥቷል። አሁን ከሌሎች ጋር አንድ ሆናችሁ ብቻ ነው ወደፊት መቀጠል የሚቻለው። እናም መርኀ ግብራችሁ ላይ ከፍተኛ እምነት ካላችሁ፤ ለአሁኑ አቆዩትና፤ ሀገር ነፃ ሲወጣ ለሕዝብ ታቀርቡታላችሁ። አሁን መታገያ ዕሴቶቻችን ተቀይረው፤ መጀመሪያ ሀገር ብለናል። ስለዚህ፤ ሀገርን እናስቀድም። የየድርጅቶቻችሁ ንብረትም ሆነ ታሪክ ይቆያችኋል። ለአሁኑ ከሌሎች ጋር በመሆን ባንድ ሰፊ የኢትዮጵያዊያን የነፃነት ንቅናቄ ሥር እንሰለፍ። በሀገር ጉዳይ ተመሣሣይና ተቀራራቢ አመለካከት ያላቸው፤ ነገር ግን የተለያየ ርዕዩት በሚከተሉ ድርጅቶች መካከል፤ የእኔ እበልጥ እኔ እበልጥ ውድድር የሚደረገው፤ ነፃ ሀገር ሲኖር፤ ሕዝቡ የመምረጥ መብቱ ሲከበርለትና፤ ሕግን የሚያከብር መንግሥት በሥልጣን ላይ ሲሆን ነው። አሁን ትግሉ ያን ለማስከበር ነው። ስለዚህ የሁሉም ባንድነት፣ ባንድ ላይ፣ ባንድ ድርጅት መሰባሰብ የግድ ነው።

 

የሸዋ አማራና ኦሮሞዎች እያለቁብት ያለው የተበከለ ሃይቅ የመንግስት እጅ አለበት ተባለ

0
0

የወያኔ ድብቅ ሴራ ሲጋለጥ የሸዋ አማራና ኦሮሞዎች እያለቁብት ያለው የተበከለ ሃይቅ የመንግስት እጅ አለመት ተባለ ቪዲዮ ይመልከቱና አሳቦን ያካፍሉ

እጂግ ብዙ ቤተሰብ የሞተበት ይህ ሃይቅ በተበከሉ ኬሚካሎች የተበረዘ ከመሆኑ የተነሳ ለመጠጥና ለተለያዩ ነገሮች የሚጠቀሙት የአካባቢው ማህበረሰቦች የቤት እንሻቶች በከፍተኛ ሁኔታ እያለቁ ነው።  የአካባቢው ነዋሪዎች  በተደጋጋሚ ለመንግስት ችግራችንን ብናስረዳም ምንም መፍሄ ኣልሰጡንም በዚህም ተስፋ ቆርጠናል በለዋል ሌላ ለመጠጥ የሚጠቀሙበት ወሃም ስለሌለ እየጠጢ መሞትን ምርጫቸው እንደኦነ በምሬት ተናግረዋል።

ftየሸዋ አማራና ኦሮሞዎች እያለቁብት ያለው የተበከለ ሃይቅ የመንግስት እጅ አለመት ተባለ

የተዋረደው ሰንደቅ አላማ ‹‹የክብር›› ቀን (ጌታቸው ሺፈራው)

0
0

ጌታቸው ሺፈራው

በዓለማችን ተፅዕኖ ፈጣሪ ከሆኑት ሰንደቅ አላማዎች መካከል የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ በቀዳሚነት ይገኝበታል፡፡ በጸረ-ቅኝ ግዛት ትግሉ ወቅት በመላው ዓለም የሚገኙ ጥቁሮች ከነጻነት ምልክትነቱም በተጨማሪ አንዳች ኃይል ያለው አድርገው ወስደውታል፡፡ በተለይ ከቅኝ ግዛት ትግሉ በኋላ በርካታ የአፍሪካና የካሪቢያን አገራት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ምልክታቸው አድርገው ተጠቅመውበታል፡፡ ከዚህም የተነሳ በሰንደቅ አላማ ላይ ጥናት የሚያደርጉ ምሁራን የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ የአፍሪካ ሰንደቅ አላማዎች ዘር ይሉታል፡፡

10482065_596327470492915_3458501353410632231_nየኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሆኑት ከዓለም ሰንደቅ አላማዎች ቀዳሚው እንደመሆኑ ለሌሎች ህዝቦች ተጽዕኖ ፈጣሪ ሆኖ በራሱ መሪዎች የተዋረደው ብቸኛው ሰንደቅ አላማም ሳይሆን አይቀርም፡፡ በርካታ የአፍሪካና የካሪቢያን አገራት የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ በምልክትነት ሲወስዱ የወቅቱ የኢትዮጵያ ገዥዎች ግን የኢትዮጵያውን ሰንደቅ አላማ ቀለም ትተው ከአውሮፓና ከአረብ አገር የተዋሱትን ሰንደቅ አላማ ክብር ከነበረው የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ጎን ያንጠለጥሏቸዋል፡፡

ሻዕቢያና ጀብሃ ሰንደቅ አላማውን ለማዋረድ (ጨርቅ ለማስመሰል) ከዓረብ አገራት በእርዳታ ያገኙት የነበረውን ዱቄትና በሰሜን ኢትዮጵያ የሚበቅለውን በለስ ቋጥረውበታል፡፡ ከሻዕቢያ ስር ሆኖ የጎለመሰው ህወሓት የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ስለማዋረድ ከሻዕቢያ ልምድ ቀስሟል፡፡ በመሆኑም እሱም እንደ ሻዕቢያ የዱቄት መቋጠሪያ አድርጎት እንደነበር ይነገራል፡፡ አቶ መለስ ዜናዊ ሰንደቅ አላማውን ‹‹ጨርቅ›› ያሉትም ከምንም ተነስተው ሳይሆን በአንድ ወቅት ሻዕቢያ ባስተማራቸው መሰረት እንደ ጨርቅ ሲጠቀሙበት ስለነበር ነው፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ ሰንደቅ አላማውን የማዋረድ ታሪክ ገና ከጫካ የጀመረ በመሆኑ ለሰንደቅ አላማው ያላው ንቀትና ጥላቻ በዚሁ መልኩ ደሙ ድረስ ዘልቆ ገብቷል ማለት ይቻላል፡፡ ለዚህም ነው አከበርኩ እያለ እንኳን ማክበር ያልቻለው፡፡

ህወሓት/ኢህአዴግ መጀመሪያ ላይ ንጹሁን ከዛም በኋላ ውሃማ ሰማያዊ ክብ ያለበት፣ በቅርቡ በ654/2001 ዓ.ም በወጣው የሰንደቅ አላማ አዋጅ ደግሞ ደማቅ ሰማያዊ መደብ ላይ ያረፈ ክብ ያለበት ሰንደቅ አላማን የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ አድርጎ እየተጠቀመበት ነው፡፡ በዚህም መሰረት በቅርብ አመታት የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል እያከበረ ነው፡፡ ከውስጥ ያልመነጨን ነገር መተግበር አይቻልምና አከብራለሁ እያለም እያወረደው ዛሬ ድረስ ደርሷል፡፡ በሌላ በኩል ገዥዎቹ ለሰንደቅ አላማ ክብር የሌላቸው መሆናቸውና የአሁኑ ሰንደቅ አላማ (በተለይ መሃል ላይ ያለው ምልክት) ያለ ህዝብ ፈቃድ መለጠፉ አሁን ‹‹የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ›› የሚባለው ህዝቡም ከላይ የተጫነበት እንጂ የራሱ እንዳልሆነ በማመኑ በሁሉም ወገን ክብር ተነፍጎታል፡፡

የዚህ ጽሁፍ አላማም ኢህአዴግ ለሰንደቅ አላማው አዋጅ አውጥቶ፣ የክብር ቀን ቆርጦ አከብረዋለሁ ቢልም ለይስሙላህ እንጂ ክብር እንደማይሰጠው ለማሳየት ነው፡፡ በሰንደቅ አላማው አዋጅ በአንቀጽ 6/1 መሰረት ‹‹ሰንደቅ አላማው ከላይ አረንጓዴ፣ ከመሃል ቢጫ፣ ከታች ቀይ›› ይኖረዋል ይላል፡፡ መሃል ላይ ያለው ኮከብ አቀማመጥንም ያስቀምጣል፡፡ ነገር ግን በየ ካፌው ሌላ ሰንደቅ አላማ (መሃል ላይ ክብ ያለውን) ከሌለው ንጹህ ሰንደቅ አላማ በማዳቀል (በክር ተሰፍቶ) የተሰቀሉት ይበልጣሉ፡፡ ምንም እንኳ በየካፌው ሰንደቁን መስቀል የማይፈቀድ ቢሆንም፣ ህጉ ተጥሶ በዘፈቀደ ተንጠልጥሎ ይገኛል፡፡

በአዋጁ ከተቀመጠው ቀለምና አቀማመጥ ውጭ የተሰቀለ ሰንደቅ አላማ በእስርና በገንዘብ እንደሚስቀጣ ተደንግጓል፡፡ ሆኖም ግን አዋጁን የደነገጉት አካላት አይጠቀሙበትም፡፡ ለአብነት ያህል አቶ መለስ ዜናዊ ከመሞታቸው ከወራት በፊት ኬንያ ላይ ሰንደቅ አላማውን ከላይ ወደታች ገልብጠውት ታይተዋል፡፡ በአዋጁ መሰረት አቶ መለስ ዜናዊ ቢያንስ በገንዘብ 3000 ብር አሊያም አንድ አመት እስር ይጠብቃቸው ነበር፡፡ ሆኖም ግን አቶ መለስ ዜናዊ ምንም ሲባሉ አላየንም፡፡

በዚሁ በማይከበረው አዋጅ 6/2 መሰረት ‹‹ቀለማቱ ብሩህና ደማቅ መሆን አለባቸው›› ይላል፡፡ ነገር ግን የተለያዩ ቁልፍ የ‹‹መንግስት›› ተቋማት ሳይቀሩ ይህን ህግ በሻረ መንገድ ሰንደቅ አላማውን ሲያውለበልቡ ይታያሉ፡፡ ለአብነት ያህል በሽብርተኝነት ተጠርጥረዋል ተብለው የሚታሰሩ ኢትዮጵያውያን የሚቀርቡበት የአራዳ ችሎት ለረዥም ጊዜ የተጠቀመበት የተበጣጠሰ ሰንደቅ አላማ (ሰሞኑን ቀይረውታል) በምሳሌነት ማንሳት ይቻላል፡፡ ከዚህም ባሻገር እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ፓርላማ ያረጀና የተቀዳደደ ሰንደቅ አላማ ያውለበልብ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ሁለቱን መስሪያ ቤቶች ጨምሮ በበርካታ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ሰንደቅ አላማው ማታ ሲወርድ አይታይም፡፡ በአራዳ ችሎትና ፓርላማውን የመሳሰሉት ምን አልባትም ከአመት በላይ ሰንደቅ አላማው ሳይቀየር ስለተሰቀለ ነው እንደዛ የተበጣጠሰው፡፡ ለይስሙላ የወጣው አዋጅ ግን ጠዋት 12 ሰዓት ተሰቅሎ ማታ 12 ሰዓት መውረድ አለበት ብሎ ደንግጓል፡፡

በአዋጁ 6/3 የሰንደቅ አላማው ወርድ የቁመቱን እጥፍ ይሆናል ይላል፡፡ በሌላ የአዋጁ ክፍልም ለህንጻዎች መሸፈኛ መሆን የለበትም ይላል፡፡ ነገር ግን በተለያዩ ካፌዎች፣ ባንኮችና የመንግስት መስሪያ ቤቶች ሰንደቅ አላማው አብዛኛውን የህንጻዎች ክፍል ሸፍኖ ይታያል፡፡ (የፈተናዎች ድርጅት ህንጻ፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ፣ አዋሽ ባንክ ላይ ማየት ይቻላል) ይታያል፡፡ በእነዚህና በሌሎች መስሪያ ቤቶችና ህንጻዎች ሰንደቅ አላማው የህንጻዎቹን አብዛኛ ክፍል ሸፍኖ (ማስጌጫ ሆኖ) ይታያል፡፡

የሰንደቅ አላማው አዋጅ አንቀጽ 10 ሰንደቅ አላማው 6 የተለያዩ መጠኖች እንደሚኖሩት ይገልጻል፡፡ 1ኛ. 210 በ420፣ 2ኛ 150 በ300፣ 3ኛ 135 በ 270፣ 4ኛ 105 በ 210፣ 5ኛ 90 በ180፣ 6ኛ 21 በ 42 ናቸው፡፡ አንደኛው በከፍተኛ አደባባይ ላይ የሚሰቀል ነው፡፡ ሁለተኛው በመካከለኛ አደባባይ ይሰቀላል፡፡ ሶስተኛው በመስሪያ ቤቶች፣ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ በትልልቅ የመንግስት ህንጻዎችና የድርጅቶች አደባባዮች የሚሰቀል ነው፡፡ አራተኛው በትልልቅ ህንጻዎች ይሰቀላል፡፡ በከፍተኛ መርከቦችና በሰልፍ ጊዜ በክብር ዘብ ይያዛል ይላል፡፡ አምስተኛው የውጭ አገር እንግዶችን ለመቀበልና በበዓላት በየ መንገዱ የሚውለበለብ ነው ይላል፡፡ በስድስተኛ ደረጃ የተቀመጠው ሰንደቅ አላማ መጠን በፕሬዝዳንቱ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩና በአምባሳደር ጽ/ቤት ጠረጴዛ ላይ እንደሚቀመጥ ይደነግጋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በፕሬዝዳንቱና በአምባሳደር መኪና ላይ 20 በ 30 ሴንቲ ሜትር የሆነ ሰንደቅ አላማ ይሰቀላል ይላል፡፡ ከተደነገገው ህግ ውጭ በሌሎች የመንግስት መስሪያ ቤቶችም (በተለየ ህግ ካልተከለከለ በስተቀር) ይሰቀላል ይላል፡፡ በካፌ፣ ጸጉር ቤት፣ ስጋ ቤት፣….ይሰቀላል ብሎ የሚደነግግ ነገር የለም፡፡ ለዛሬው በዓል ግን እነዚህ ቤቶች በተለያየ ቁመትና ወርድ ሰንደቅ አላማ ከቀበሌ ታድሏቸው በየ ቦታው አንጠልጥለውታል፡፡

ትልቁ ሰንደቅ አላማ (210 በ420) በአደባባይ የሚሰቀለው ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ትልቁ ከ2 እስከ አራት ሜትር ተኩል ብቻ እንደሚሆን የሚያሳይ ነው፡፡ ሆኖም የመንግስት መስሪያ ቤቶችና ባንኮች አብዛኛውን ህንጻቸውን ያስዋቡት እንዳለ ሆኖ ለዛሬው በዓል የቀበሌ መዝናኛዎች፣ ካፌዎችና ሌሎች ንግድ ቤቶች ከአንደኛው በረንዳ ጫፍ እስከ ሌላኛው በረንዳ ጫፍ የሰቀሏቸው ሰንደቅ አላማዎች በአንደኛ ደረጃ ከተቀመጠው በብዙ እጥፍ የሚበልጡ (የሚረዝሙ) ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ በተለያዩ ንግድ ቤቶች አንዳንዶች ከግራ ቀደ ቀኝ አረንጓዴ፣ ቢጫ ቀይ አሊያም በተገላቢጦሹ ሰቅለውታል፡፡ ካድሬዎቹን ለማስደሰት እንጅ የሚያምኑበት ብዙዎቹ ባለመሆናቸው አንዳንዶቹ ታዛው ላይ፣ ሌሎቹ መስኮት አሊያም ያገኙት ቦታ ላይ መሬት እስኪነካ አንዘላዝለውታል፡፡

በአዋጁ አንቀጽ 16 የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ከላይ በተደነገገው መሰረት አንድ አይነት ነው ይላል፡፡ ነገር ግን ለዛሬው በዓል ከተሰቀሉት መካከል በአሁኑ አዋጅ የተቀየረው መሃሉ ላይ ውሃማ ሰማያዊ ያለበትም በስፋት ተሰቅለው ይገኛሉ፡፡ አንቀጽ 17 ሲያረጅ፣ ሲበላሽ ወይንም በሌላ መንገድ በክብር ይቃጠላል፤ ይቀበራል ቢልም ይህ ግን ሲሆን አይታይም፡፡ አንቀጽ 18 ሰንደቅ አላማው ከክልል ሰንደቅ አላማዎች ጋር የሚሰቀልበትን መንገድ የተዘረዘረበት ነው፡፡ ከፍ ብሎ መሰቀል አለበት፡፡ ከሁለት ጋር ቢሆን መሃል ላይ ይሆናል፡፡ ከሁለት በላይ ከሆኑ በስተቀኝ በኩል መጨረሻ ሆኖ ይውለበለባል፡፡ ይህም ቢሆን ሰንደቅ አላማው ውስጣቸው በሌለው ገዥዎች ዘንድ የሚታወስ አይደለም፡፡ ለአብነት ያህል ስድስት ኪሎ አካባቢ የሚገኘው የኦሮሚያ የፍትህ ቢሮ ላይ ሁለት የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማዎች ያውም ያሰቃቀሉን ህግ በማያሟላ መልኩ ከክልሉ ሰንደቅ አላማ ዝቅ ብሎ ተሰቅሏል፡፡

አንቀጽ 22 በማኝኛውም ጊዜ ሰንደቅ አላማው ዝቅ ብሎ አይውለበለብም ይላል፡፡ እነሱ ግን በየ ጉራንጎሩ ሲፈልጉ ገልብጠው ያውለበልቡታል፡፡ ምንም እንኳ በፕሬዝዳንቱ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩና አምባሳደሩ መኪና ብቻ እንደሚውለበለብ ቢደነገግም ለዚህ በዓል ሲባል ታክሲና ባባጆች ሳይቀር እንዲያውለበልቡ ታድሏቸዋል፡፡

አንቀጽ 22 ሰንደቅ አላማ በቀብር ወቅት መሆን ስላለበበት ሁኔታ የሚገለጽበት ነው፡፡ በአንቀጹ ‹‹ቀብሩ ከመፈጸሙ በፊት በአስከሬን ሳጥኑ ላይ ያረፈው ሰንደቅ አላማ በተገቢው ስነ ስርዓት ተጣጥሮ መነሳት ያለበት ሲሆን በማንኛውም መልኩ መሬት መንካት የለበትም›› ይላል፡፡ ነገር ግን በአንድ ወቅት ጨርቅ እንዲመስል ዱቄት የቋጠሩበት፣ ከዛም ጨርቅ ብለው የዘለፉት፣ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ገልብጠውት የታዩት አቶ መለስ ዜናዊ አስከሬን ላይ ሲቀበር ሁላችንም በቴሊቪዥን ያየነው ኃቅ ነው፡፡

ህወሓት/ኢህአዴግ በሰንደቅ አላማው ላይ ይህን ያህል ኃጢያት ሲሰራ አንድም ቀን ይቅርታ ጠይቆ አያውቅም፡፡ ይህን ሁሉ ሲሰራ ማንም ጠይቆት አሊያም ተቀጥቶ አላየንም፡፡ በተቃራኒው ግን ለሰንደቁ እንደቆመ ለማሳየት ይሞክራል፡፡ የዛሬው በዓልም ለማያምንበትና በውስጡ ለሌለው ሰንደቅ አላማ ክብር እሰጥበታለሁ የሚለው እንዲህ ከራሱ ህግ ጋር እየተቃረነ እና እያዋረደው ነው

ሰልጣኝ ተማሪዎች በፌደራል መደብደባቸው ታወቀ * ተቃውሞ አስነስተዋል የተባሉት ተማሪዎች ታስረዋል

0
0

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ወስደው የውሎ አበል ያልተከፈላቸው የመጀመሪያ አመትና ነባር ሶስተኛ ዙር ሰልጣኞች ‹‹የውሎ አበላችን ይሰጠን›› በሚል ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣታቸው በትናንትናው ዕለት በፌደራል ፖሊስ መደብደባቸውን ተማሪዎቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ሰላማዊ ሰልፉን አደራጅታችኋል የተባሉ በርከት ያሉ ተማሪዎች መታሰራቸውንም ታውቋል፡፡
Negere Ethiopia
ስልጠናውን አርብ መስከረም 30/2007 ዓ.ም የጨረሱ ሲሆን መጀመሪያ ላይ እንደሚከፈላቸው ቃል ተገብቶላቸው የነበረው የውሎ አበል አይከፈላችሁም በመባላቸው በትናንትናው ዕለት ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል፡፡ ተማሪዎቹ አበሉ አይከፈላችሁም ቢባሉም አሰልጣኞቻቸው ‹‹ገንዘቡ መጥቷል፡፡ አንከፍልም የሚሉት ዝም ብለው ነው›› ማለታቸው ተማሪዎቹ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲወጡ ገፋፍቷል ተብሏል፡፡ የፌደራል ፖሊስ ሴት ተማሪዎች ከግቢው እንዳይወጡ የከለከለ ሲሆን ወንድ ተማሪዎች ከግቢው እንዲወጡ ከተደረጉ በኋላ መደብደባቸውንና መታሰራቸውን ተማሪዎቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

የደኢህዴን 22 አመት ምስረታን ተከትሎ በሀዋሳ በርከት ያለ ፌደራል ፖሊስ እንደነበርና ተማሪዎቹ አበላቸው እንዲከፈላቸው በጠየቁበት ወቅት ‹‹ከተማው ውስጥ ፌደራል ሞልቷል፡፡ እናስደበደባችኋለን›› እያሉ ያስፈራሯቸው እንደነበር ታውቋል፡፡


በአባላት ቅሬታ እና ነቀፌታ ሃላፊነቱን የለቀቀ የፓርቲ መሪ ቁ.ር 1

0
0

ይድነቃቸው ከበደ

“ልዩነት የግድ ጥላቻን ወይም ድብድብን ማስከተል አለበት ብለው የሚያምን እና የሚያስብ በድርጊቱም የሚገፉ ካለ ከባድ ስዕተት ነው፡፡ ፣ልዩነትን በአንድ ጊዜና ሙሉ በሙሉ ማጥፋት ባይቻልም በሰለጠነና በሰከነ አካሄድ በውይይትና በሀሳብ ልውውጥ ማጥበብ ይቻላል፡፡” ለዚህም ይመስላል አንድነት ፓርቲ ውስጣዊ ችግሩን ሙሉ ለሙሉ ባይባልም መሠረታዊ ችግሩን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት የቻለው፡፡ የዚህም ጥሩ ማመላከቻ የሚሆነው ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው በገዛ ፍቃዳቸው ሃላፊነታቸውን መልቀቃቸው እና በምትካቸው የአብዛኛውን የፓርቲ አባል መልካም ፍቃድ ያገኙት፣ አቶ በላይ በፍቃዱ መመረጣቸው ነው፡፡ይህ ደግሞ ለአመራር ለውጥ የተሄደበትን መንገድ በአብዛኛው ጤናማ ለመሆኑ በቂ መረጃ ነው፡፡

ይድነቃቸው ከበደ

ይድነቃቸው ከበደ


እርግጥ ነው በሂደቱ እንደ መልካም ተሞክሮ ለመውሰድ የሚቸግሩ፣ ጠቃሚ ያልሆኑ የሃሳብ ልውውጦች ለማየት እና ለመታዘብ ተችሎአል፡፡በተለይ በኢ/ር ግዛቸው የስራ አፈፃፀም ደስተኞች ባልነበሩ በተወሰኑ የፓርቲው አባላት የታዩ ችግሮች መኖራቸው የማይካድ ሃቅ ነው፡፡ይሁን እንጂ በፓርቲው አባላቶች እና አመራሮች እንዲሁም በድጋፍ ሰጪዎች ከባድ ጥረት የተገኘው ውጤት፤ያለፈው ስዕተት በማስታወስ ዋጋውን የሚያስቀንሰው አይደለም ! በመሆኑም አሁን ላይ ለደረሳችሁበት አስደሣች ውጤት እንኳን ደስ አላችሁ ላለማለት ለውጥ ፈላጊ ለሆነው ሁሉ ለዴሞክራሲ ሃይሎች ምክንያት ይኖራል ብዬ አልገምትም፡፡

ይበልጥ ደግሞ ሂደቱን ለየት የሚያደርገው ኢ/ር ግዛቸው በገዛ ፍቃዳቸው ከስልጣናቸው መልቀቃቸው ሳይሆን የለቀቁበት መንገድ ነው፡፡ ለሁላችንም ግልፅ እንደሆነው ሁሉ አብዛኛው የአንድነት ፓርቲ አባላት በኢ/ር ግዛቸው የስራ አፈፃፀም እና ውሣኔ አሰጣጥ ደስተኞች አልነበሩም ፡፡ሆኖም ግን ምንም ጊዜ ቢወስድም “በእኔ የሰራ አፈፃፀም ደስተኛ ባለመሆናችሁ፣ ከምንም በላይ ደግሞ ፓርቲው ስለሚበልጥ ሃላፊነቴን በገዛ ፍቃዴ ለቂቃለው” ማለታቸው እና ውሳኔቸውን ተግባራዊ ማድረጋቸው ለኢ/ር ግዛቸው አድናቆትን የሚያሰጥ ነው፡፡

ከምንም በላይ ግን በኢትዮጵያ የ23 ዓመት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጉዞ በአባላት ቅሬታ እና ነቀፊታ ከስልጣን ዘመኑ በፊት ሃላፊነቱን የለቀቀ የፓርቲ መሪ ቁጥር አንድ ሊያስብል የሚያስችል ታሪክ ኢ/ር ግዛቸው ለማስመዝግ ችለዋል፡፡ ይህ ማለት ግን የኢ/ሩ የቀድሞ ስዕተቶች ይረሳሉ ማለት አይደለም፡፡ለቁጥር የበዛ በማወቅም ባለማወቅም በኢትዮጵያ የተቃውሞ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የሰሯቸው ስዕተቶች አሉ፡፡ በተለይ ዛሬ ላይ ሆነው የሰሩት መልካም ስራ ማለትም የአባለት ቅሬታ እና ነቀፌታ የማዳማጥ ልምድ “ያኔ ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም ያካተተው የ “መርህ ይከበር” ጥያቄ ወቅት አድርገውት ቢሆን ኖሮ አንድነት ፓርቲ ብቻ ሣይሆን የኢትዮጵያ የተቃዋሚ እንቅስቃሴ ከፍ ከማለትም ባለፈ ፤አሁን ካለበት ደረጃ በእርግጠኝነት የወያኔን የአገዛዝ ሥርዓት ጭርሶ ባያጠፋውም የሚያሽመደምደው ነበር፡፡
GizachewShiferaw
በመሆኑም ሰው በገባው ልክ የሚኖር ፉጡር እንደመሆኑ መጠን በገባቸው ቀን የሚገባቸውን በማድረጋቸው እኔም ብሆን አድናቆቴን ለመግለፅ እገደዳለው፡፡ አሁን ላይ በመሆን የባለፈውን በማንሳት ለተጀመረው ሁለንታናዊ የሰላማዊ ትግል ወደፌት ፈቀቅ የማያደርግ፣ ማናቸውን ነገሮች ማንሣት አስፈላጊ እንዳልሆን፤ መገመት ቀላል ነው፡፡ ሆንም ግን ችግሮችን ማስታወስ ክፋት አይኖረውም፡፡ስለዚህም ዛሬ አንድነት የደረሰበት አስደሳች ውጤት ያለፉትን ስዕተቶች ድርጅታዊ ለውጥ ለማምጣት እንደግባት ከመጠቀም ሊያግደው የሚችል ነገር አይደለም ለማለት ያስደፍራል፡፡

አንድነት ዛሬ ከችግሮች መካከል አንዱን ቀረፍ እንጂ ሙሉ በሙሉ ውስጣዊ የፓርቲ ችግሮችን ፈታ ማለት አይደለም፡፡ከዚህ ቀደም የነበረ፣አሁን ደግሞ የተገኘውን ውጤት መሠረት ያደረገ በራሱ የሚፈጠር ብዙ ችግሮች ይኖራሉ፣ውጫዊ የገዥው ሥርዓት ተፅኖ እንደተጠበቅ ሆኖ ፡፡ ስለዚህም አዲሱ የፓርቲው ሊ/ቀ ወጣቱ በላይ ፍቃዱ ከፍተኛ የሆነ ስራ ይጠብቀዋል፣ በተለይ ደግሞ የእሱ የሃሳብ ተቀናቃኝ የሆኑት የአንድነት ፓርቲ አባለት ከበሆደ ሰፊነት ባለፈ ሃሳባቸውን ሊሰማቸው እና በተግባር ሊያሳትፋቸው ይገባል፡፡በይበልጥ ደግሞ ከሌላ አቻ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር መዋቅራዊ ወይም የስራ ግንንነቶች በይበልጥ እንዲፈጠሩ የማድረግም ሃላፊነት ጭምር አለበት፡፡በአሰራሩም ግልፅነት እና ተጠያቂነት ያለው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሲያቆቁም ሥራን እንጂ ሌላ የጎንዩሽ ጥቅምን መሠረት ያላደረገ መሆኑ ማረጋገጥ አለበት፡፡ኢ/ር ግዛቸውም በፓርቲያቸው ውስጥ አቅማቸው እና ጊዚያቸው በፈቀደው መልኩ የማገልገልም ሃላፊነታቸውም እንደተጠበቀ ነው፡፡

በመጨረሻም ለአንድነት ፓርቲ አባለት፣አመራሮች ፣ድጋፍ ሰጪዎች እና ለአዲስ ወጣቱ ሊ/ቀ በላይ ፍቃዱ ለደረሳችሁበት ውጤት እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለው! ይህ የግሌ የሆነው ሃሳብ ከማጠቃለሌ በፊት የጋሽ መስፍን “ሥልጣን ባህልና አገዛዝ ፖለቲካና ምርጫ” ከሚለው መፃፈቸው ገፅ 32 የሚገኘውን ፅሑፍ ሁላችንም ት/ት እንድንወስድበት በመጋበዝ ነው፡፡ “እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ወደ ፖለቲካ ሲገባ ከልጅነት እስከ እውቀት በውስጡ የተመረገውን ጌትነትና የሎሌነት ባህል ፍቆ ፈቅፍቆ ማረገፍ አለበት፡፡ በግድ የአስተሳሰብ የጽዳት ዘመቻ ያስፈልገናል፡፡ ዓላማን የማጥራት ዘመቻ ያስፈልገናል፡፡ በግድ የነጻነትና የእኩልነት አራማጆች በቁርጠኝነት መነሳትና ማሳየት ያስፈልገናል፡፡ ብዙዎች የተቀናቃኝ መሪዎች ላይ የሚታየው የድሮው መኳንንትና መሳፍንት ለመምሰል የመሞከር ጠባይና ከዚህም ጋር ተያይዞ ሎሌዎችን በገንዘብ ሆነ በወደፊት ተስፋ እየገዙ የአገዛዝን ባህል ለማራመድ የሚደረገው ሙከራ የፖለቲካውን ሥርዓት አያራምድም፡፡ ጥረቱ ሁሉ በሥልጣን ላይ ያሉትን ሰዎች ለመለወጥ እንጂ ሥርዓትን ለመለወጥ አይመስልም፡፡”

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !!!

ሰቆቃወ ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም- ኢትዮጵያዊ

0
0

በዲ/ን ተረፈ ወርቁ

የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራን እስራኤላዊውን ነቢዩ ኤርምያስን ‹‹አልቃሻው ነቢይ›› በሚል ሰቆቃና ምሬት፣ ዕንባና ኀዘን ዕጣ ፈንታው የሆነበት የመከራ ሰው ሲሉ በዚህ ቅፅል ስም ይጠሩታል፡፡ ለነገሩ ራሱ ነቢዩም ቢሆን ስለ እስራኤል፣ ስለ እናት ምድሩ የታሪክ ስብራት አሊያም ፕሮፍ እንደሚሉት ‹‹የታሪክ መክሸፍ››፣ ስለ ሕዝቦቹ ስደት፣ መከራና ውርደት አነባ ዘንድ ምናለ ዓይኖቼ ሳያቋርጥ እንደሚፈልቅ የምንጭ ውኃ በሆኑልኝ ሲል የለመነና የተመኘ፣ የአገሩ ውርደት፣ የሕዝቡ መጎሳቆልና መዋረድ በእጅጉ እረፍት የነሳው ጻድቅና እውነተኛ ነቢይ ነበር፡፡ ነቢዩ በዚህ ተማጽኖውና ሰቆቃውም፡-
ስለ እስራኤል የታሪክ ስብራት/መክሸፍ፣ ስለ ሕዝቦቿ፣ ነገሥታቶቿ፣ ካህናቶቿና ሐሰተኛ ነቢያቶቿ ኃጢአትና ዓመፃ፣ በደልና ግፍ፣ የትውልዱ ውርደትና ጉስቁልና እንዲህ ሲል አንብቷል፣ ‹‹… ስለ ወገኔ እስራኤል ሴት ልጅ ቅጥቃጤና መከራ ዓይኔ በእንባ ደከመች፣ አንጀቴም ታወከ፣ ጉበቴም በምድር ላይ ተዘረገፈ፡፡›› በማለት ስለ ወገኑ፣ ሕዝቡና ምድሩ ነቢዩ ኀዘኑ ምን ያህል የከፋና የአገሩ ዕጣ ፈንታም ልቡን ምንኛ ክፉኛ ሰብሮት እንደነበር ‹‹የሰቆቃወ ኤርምያስ›› መጽሐፍ ይተርክልናል፡፡
ፍርድን በሚያዛቡ፣ ድሀን በሚበድሉና በሚያጎሳቅሉ፣ መበለቲቱንና ድሀ አደጉን በሚገፉ፣ ፍትሕን በሚያዛቡ አድር ባይ ሙሰኞቿ፣ የሕዝባቸውን ደም በከንቱ በሚያፈሱ ጨካኝ ነገሥታቶቿ፣ ኃጢአትን እንደ ውኃ በሚጨልጡ ካህናቶቿ፣ ሐሰተኛና ለባጭ በሆኑ ነቢያቶቿ፣ እውነትን በአደባባይ በሚረግጡ ገዢዎቿና ፈራጆቿ ምክንያት የአምላኳ ቁጣና መዓት በፈሰሰባት በእስራኤል፣ በአይሁዳውያኑ ሕዝቦች ‹‹የታሪክ መክሸፍ›› ታላቅ የትውልድ ኪሳራና ውርደት የተነሣ ነቢዩ ኤርምያስ የዕንባ፣ የሰቆቃ ሰው ‹‹አልቃሻው ነቢይ›› የሚል ስያሜ እንደተሰጠው የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡
በዚህ አጭር መጣጥፌ ፕ/ር መስፍንን እንደ እስራኤላዊው ነቢዩ ኤርምያስ የዕንባና የሰቆቃ ሰው ስላልኩበት ጉዳይ ወይም የታሪክ ተመሳስሎ አንዳንድ እውነታዎችን ላነሣ ወደድኹ፡፡ ለዚህ አጭር ጽሑፌ መነሻ የሆነኝ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም ከሸገር 102.1 ሬዲዮ የቅዳሜ ጨዋታ ዝግጅት ላይ ከመዓዛ ብሩ ጋር ያደረጉት ለሰባት ሳምንታት የዘለቀ ቆይታቸው ነው፡፡

Prof. Mesfin Woldemariam

Prof. Mesfin Woldemariam


በሸገር 102.1 ሬዲዮ በቅዳሜ የጨዋታ እንግዳ ዝግጅት ላይ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ ከእውቁ ምሁር፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች፣ ታሪክ ተመራማሪ፣ ፖለቲከኛ፣ ጸሐፊና ገጣሚ ከሆኑት ከአዛውንቱ ከፕ/ር መስፍን ጋር ያደረገችውን ቃለ መጠይቅ በታላቅ ጉጉትና ስሜት ውስጥ ሆኜ ነበር የተከታተልኩት፡፡ ፕ/ር መስፍን ለተከታታይ ሰባት ሳምንታት ከሸገር ሬዲዮ ጋር ያደረጉት ቆይታ አስደሳች፣ አስተማሪ፣ መካሪ፣ አዝናኝ፣ በአንጻሩ ደግሞ አሳዛኝ፣ የሚያስቆጭ፣ የሚያናደድ፣ በኀዘን፣ በቁጭትና በጸጸት ብግን የሚያደርግ፣ ቀቢጸ ተስፋ የተጫነው ባለ ብዙ ኅብር፣ ባለ ቡዙ መልክ ነበር ማለት ይቻላል፡፡
ፕሮፌሰሩ ከመዓዛ ጋር በነበራቸው ቆይታ ከልጅነት እስከ አሁን ዕድሜያቸው ድረስ ያሳለፉትንና የሚያስታውሱትን ትዝታቸውን ለዛ ባለው አንደበት ከገጠመኛቸው ጋር አዋዝተው ሊያጋሩን ሞክረዋል፡፡ ፕሮፌሰር እምነታቸውን፣ የሕይወት ፍልስፍናቸውን፣ ጽናታቸውን፣ ትዕግሥታቸውን፣ ወኔያቸውን፣ ውስጣዊ ስሜታቸውን፣ ኀዘናቸውን፣ ጸጸታቸውን፣ ብሶታቸውንና… እንዲሁም በማይጠፋና ሕያው በሆነ የፍቅር ማኅተም በውስጣቸው ለታተመችው ለውድ አገራቸው ኢትዮጵያና ለሕዝባቸው እንዲሆን የሚመኙለትን ሕልማቸውንና ምኞታቸውን ኀዘንና ብሶት እያበስለሰላቸው ቁጭትና ጸጸት በተቀላቀለበት ስሜት የልባቸውን አውግተውናልና እናመሰግናቸዋለን!!
ፕ/ር መስፍን ከሸገር ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታቸው ለዕንባ፣ ለለቅሶ ቅርብ የሆኑ፣ አሁንም ድረስ የሰቆቃና የትካዜ ሰው መሆናቸውን በሚገባ እንድገነዘብ አድርጎኛል፡፡ ፕ/ር በዚህ የጨዋታ እንግዳ ቆይታቸው እንደ አይሁዳዊው የእግዚአብሔር ነቢይ ኤርምያስ በተለያዩ ጊዜያት በጸጸትና በቁጭት ዕንባቸው እንዲፈስና ነፍሳቸው ትካዜ ውስጥ እንዲገባ ያደረጋቸው ግላዊና አገራዊ የሆኑ ትዝታዎቻቸው፣ አገራችን በረጅም ዘመን ታሪኳ ያለፈችበትና አሁንም ገና በቅጡ ያልተላቀቅናቸው ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ቀውሶቻችን ለዚህች አጭር መጣጥፌ ዐቢይ ምክንያት ኾኖኛል፡፡
እኚህ ኢትዮጵያዊ ምሁር ሦስት መንግሥታትን ባፈራረቁባት እናት ምድራቸው ያሳለፉት፣ አሁንም በዘመናቸው እያዩትና እየሰሙት ያለው ማለቂያ የሌለው የሚመስለውና መፍትሔውን አገኘነው ስንለው እየራቀን ያስቸገረን የኢትዮጵያችን ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ፣ በየቤተ እምነቶች የነገሠው የሞራል ውድቀትና ዝቅጠት፣ የመንፈሳዊነት ድርቅ፣ ዘርኝነቱ፣ በሥልጣን መባለጉ፣ ሙሰኝነቱ፣ የፍትሕ እጦቱ፣ ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ የቀጠለውና ድኃውን ኅብረተሰብ ግራ ያጋባው የኑሮ ውድነቱ… ወዘተ ለፕሮፌሰሩ የሰቆቃና የእንጉርጉሮ፣ የብሶትና የትካዜያቸው ምክንያት የኾናቸው ይመስላል፡፡
ፕ/ር መስፍንን ባሳለፉት የሕይወት ዘመናቸው ክፉኛ ውስጣቸውን በኀዘን ጦር የወጋውና ዛሬም ድረስ ሲያስታውሱት ውስጣቸውን የሚረብሻቸውና ብርቱ ኀዘን ካጫረባቸው አገራዊ፣ ታሪካዊ ክስተት መካከልም የትውልድ እልቂት፣ የአገር ውርድት ወይም የፕሮፍን አገላለጽ ልዋስና የኢትዮጵያችን ‹‹የታሪክ መክሸፍ›› አንዱና ዋንኛ መለያ ተብሎ ሊጠራ የሚችለው እራሳቸው ፕሮፌሰር በዓይናቸው ዐይተው ምስክር የሆኑበትና የታዘቡት በአገራችን በተለይም በሰሜኑ ኢትዮጵያ ግዛት እንደ እርሳቸው አገላለጽ ‹‹ችጋር›› ያስከተለው ዘግናኝ እልቂትና ዓለምን ሁሉ እንባ ያራጨው የ፲፱፻፷፮ቱ ራብ ነው፡፡
ፕ/ር በዚህ አገራችን ኢትዮጵያ በዓለም ሁሉ ፊት ስሟን የቀየረውና የራብ፣ የእልቂት ምድር፣ አኬል ዳማ- የደም ምድር ተብላ እንድትጠራ፣ ሕዝቦቿም በኼዱበት ዓለም ሁሉ አንገታቸውን እንዲደፉ ምክንያት ስለሆነው የችጋር ርእሰ ጉዳይ ላይ በአገር ውስጥና በውጭ አገር በሚገኙ ስመ ጥር በሆኑ እንደ ሀርቫርድ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ሳይቀር ሰፊና ጥልቅ የሆነ ምርምርና ጥናት እንዳደረጉ አጫውተውናል፡፡
ይህ ክፉ ዘመን፣ ይህ ክፉ ራብ የሠራልኝ ሥራ፣
አባቴን ለስደት እናቴን ለአሞራ፡፡

የወንድ ልጅ እናት ታጠቂ በገመድ
ልጅሽን አሞራ እንጂ አይቀብረውም ዘመድ፡፡
ተብሎ አገሬው በታላቅ ኀዘንና ብሶት የተቀኘለት የራብና የእርስ በርስ ጦርነት የደም ታሪካችን ዛሬም ድረስ በጸጸትና በቁጭት የምናስታውሰው ነው፡፡ ይህ አሳፋሪ፣ ዘግናኝና አሳዛኝ የታሪክ ስብራትና የትውልድ እልቂት ፕ/ሩን አገሪቱን ‹‹የከሸፈ ታሪክ ባለቤት›› እስከ ማለት አደርሷቸዋል፡፡ እናም ዛሬም ድረስ በአዛውንቱ በፕ/ር መስፍን ልብ ውስጥ እማማ ኢትዮጵያ በውስጣቸው በምሬትና በብሶት የሚያነቡላት፣ ሙሾ የሚደረድሩላት የነፍሳቸው ስብራት፣ ሕመምና ስቃይ ሆና እንደዘለቀች ነው፡፡ ዛሬም በእኚህ አዛውንት ስለ እናት ምድራቸው ኢትዮጵያ ያላቸው ተስፋ ያለቀ፣ የተቆረጠ ነው የሚመስለው፡፡
ሌላኛው ፕሮፌሰር ከመዓዛ ጋር ባደረጉት የመጀመሪያው ሳምንት ቆይታቸው እስካሁንም ድረስ ውስጣቸውን በቁጭትና በጸጸት የሚያንገበግባቸው የዘጠኝ ወር ቤታቸው ለሆኑት፣ በመልካም ሥነ- ምግባር ተቀርጸው እንዲያድጉ ትልቅ መሠረት ለጣሉላቸው ለወላጅ ለእናታቸው የሚገባቸውን ውለታ ሳያደርጉላቸው በሞት የመለየታቸው ጉዳይ እንደሆነ እንባና ሳግ በተቀላቀለ ስሜት አጫውተውናል፡፡
እኚህ ዕድሜ ባለጠጋ በሆኑ አዛውንትና አንጋፋ ምሁር ስለ እናታቸው ባሰቡ ቁጥር ዓይናቸውን በሚሞላው እንባቸውና ውስጣቸውን በሚያብሰለስላቸው ጸጸትና ኀዘን ውስጥ በፕሮፌሰሩ የልባቸው ዙፋን ላይ የነገሠችውና የትካዜያቸውና የሰቆቃቸው ምክንያት የኾነችው የትልቋና የሁላችንም እናት የሆነችው የምድራችን፣ የእማማ ኢትዮጵያ ኀዘንና ትካዜ፣ ብሶትና ሰቆቃ የሞላበት የተዥጎረጎረ የታሪኳ ገጽ ተራ በተራ፣ ምዕራፍ በምዕራፍ እየተገለጸ ከፊታችን ድቅን እንደሚልብን አስባለሁ፡፡
እናም ፕሮፍ ለሰባት ሳምንት በዘለቀ የቅዳሜ ጨዋታቸው ይኸውን የተዥጎረጎረ፣ በደም የቀላ የኢትዮጵያን ታሪክ እያነሡ፣ እየፈተሹና እንያንገዋለሉ ‹‹የታሪካችንን መክሸፍ››፣ የሕዝባችንን ውርደትና ጉስቁልና እንደ አይሁዳዊው ነቢዩ ኤርምያስ በእንባ፣ በኀዘንና በሰቆቃ ተውጠው ተረኩልን፡፡
ፕሮፌሰር መስፍን አክለውም የራብና የእርስ በርስ ጦርነት፣ የእልቂት ምድር-አኬል ዳማ በሚል ስያሜ የጠለሸውን የትናንትና መልካም ታሪኳን፣ ስሟንና ክብሯን ለመመለስና ለተሻለ ነገ ጉልበቴ በርታ በርታ እያለች ያለችውን እናት ኢትዮጵያን የእግር እሳት ሆኖ እየለበለባትና አላንቀሳቅሳት ያለ ሌላ የዘረኝነት/የጎሰኝነት ክፉ አደጋ እንደተጋረጠባት በስጋት ስሜት ሆነው ነገሩን፣ ውስጣቸውን ክፉኛ ፍርሃት፣ ቁጭትና ሥጋት እያረሰው፡፡ እናም ከዚህ ዙሪያችንን ከከበበን ክፉ አደጋ አገሪቱን ይታደጉ ዘንድ በሥልጣን ላይ ላሉት ሰዎች አስተዋይና ይቅር ባይ ልቦናን ፈጣሪ ይቸራቸው ዘንድም ፕሮፌሰር በሸገር የቅዳሜ እንግዳ ቆይታቸው ከልብ ለምነዋል፣ ተማጽነዋል፡፡
ለፕሮፌሰሩ ከወዲሁ ስለ ነገይቱ ኢትዮጵያ የታያቸው ምስል ዝብርቅርቅ ያለ፣ ጥፋትን ያዘለ፣ የማይስብ፣ አንዳች ውብና አዲስ ተስፋ የማይንጸባረቅበት፣ አሳሳቢና ድንግዝግዝ ይመስላል፡፡ እናም በፕሮፌሰር ልብ ውስጥ ብዙ ሐዘን፣ የማያቋርጥ ጭንቀት፣ በቃላት ሊገለጽ የማይችል ቁጭትና እልህ የሚንጠው ብርቱ የነፍሳቸው ጩኸት ስለ እናት ምድራችን ኢትዮጵያ በቃለ ምልልሳቸው ውስጥ በለሆሳስ ተሰማኝ፣ አሊያም ቁጭታቸውንና ሐዘናቸውን ለምንጋራ ሁሉ እንዲያ እንደሚሰማን ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እኔም የኸው የፕሮፌሰሩ ሰቆቃና ብርቱ ኀዘን ነው ብዕሬን እንዳነሳ የገፋፋኝም፡፡
በእርግጥም እኚህ የዕድሜ ባለጠጋ፣ ምሁር አዛውንት የዕድሜያቸውን ግማሽ ማለት ይቻላል ስለ እናት ምድራቸው፣ ኢትዮጵያ ልባቸው በኀዘን ጦር እንደተወጋ፣ ዓይናቸው ዘወትር እንዳነባ፣ እንደ አይሁዳዊው የእግዚአብሔር ነቢይ ኤርምያስ የምሬትና የብሶት፣ የትካዜና የሰቆቃ ሰው ሆነው አብዛኛው ሕይወታቸውን ዘመን እንደፈጁ ነው በቃለ ምልልሳቸው የነገሩን፣ ያጫወቱን፡፡
እናም ፕሮፌሰር ታሪኳ ሁሉ የከሸፈ ነው፣ የልማት፣ የዕድገትና የብልጽግና ጎዳናዎቿ ሁሉ በእሾህ የታጠሩባት ናት፤ እንዲያም ሲል ደግሞ ‹‹በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ›› እንዲሉ ሌላ ውስጥ ለውስጥ እየነደደ ያለ ሞትን፣ ጥፋትንና እልቂትን የደገሰልን የዘረኝነት፣ የመለያየት አደጋ ተጋርጦባታል ለሚሏት አገራቸው ኢትዮጵያ ሥጋታቸውና ጭንቀታቸው እጅጉን የበረታ፣ ያየለ ነው የሚመስለው፡፡
ይህች በፕሮፌሰሩ ሕሊና ውስጥ የዘመናት ታሪክ ልቃቂት ውሏ ሲተረተር፣ ሲገለጽ ከከሸፈ ታሪክና ገድል በቀር ሌላ ታሪክ የሌላት፣ እድገትና ብልጽግናን ያዝኳቸው ስትላቸው የሚያመልጧት ነጻነትና ሰላም፣ ፍትሕና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ብሎ ነገር ሕልም የሆነባት፣ በእርስ በርስ እልቂት፣ በፍጅትና በራብ የምትታወቅ፣ በአብራኳ ክፋዮች፣ በገዛ የማኅፀኗ ልጆቿ ደም የምትዋኝ፣ በደም ሸማ፣ በደም ሰንደቅ የደመቀች፣ በደም ታሪክ የተንቆጠቆጠች የተባለች ኢትዮጵያ- ምስሏም፣ ገጽታዋም ይኽው ነው በፕሮፌሰር መስፍን ልብ፣ እይታና የረጅም ዓመታት ትዝታቸው ትርክት ውሰጥ፡፡
በማብቂያዬም ይህን ሰቆቃወ ፕ/ር መስፍን-ኢትዮጵያ ብዬ የሰየምኩትን አጭር መጣጥፌን በእንዲህ ቀቢጸ ተስፋ ባየለበት የጨለምተኝነት መንፈስ ልደምድመው አልወደድኩም፡፡ በፕሮፌሰር መስፍን እይታ የረጅም ዘመን ታሪክ መዝገቧ ሲከፈት በአብዛኛው ‹‹የከሸፈ ታሪክ›› ባለቤት ናት ብለው ስለሚጠሯት ኢትዮጵያ ታሪክ አንድ የሚግረን ትልቅ ሐቅ እንዳለ ለማንሣት እወዳለኹ፡፡
ይኸውም ይህች አብዛኛው ታሪኳ የከሸፈ ነው፣ ሞተች በቃ፣ ከአሁንስ ወዲያ ተስፋም የላት የተባለች ኢትዮጵያ፣ በተለያዩ ዘመናት ከመውደቅ፣ ከውርደት፣ ከሽንፈት ታሪኳ እንደገና የተቀበረችበትን አፈር አራግፋ ዳግም በአዲስ የዘመን ብስራት ትንሣኤ ብድግ ያለችበት ወርቃማ የታሪክ ዘመንም እንደነበራት ማሰብ፣ ማስታወስ ያለብን ይመስለኛል፡፡
ይህን አሳቤን የሚያጠናክርልኝ አንድ የጥናት ወረቀት እዚህ ላይ ማነሣቱ ተገቢ ይመስለኛል፡፡ ራሳቸው ፕ/ር መስፍን ተሳታፊ በነበሩበት በ1997 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማኅበር ባዘጋጀው ‹‹Vision 2020›› በ2020 ልናያት የምንፈልጋት ወይም የምንመኛት ኢትዮጵያ በሚል የውይይት መድረክ ላይ የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ፡- ‹‹ምን አለምን? የት ደረስን? ወዴትስ እያመራን ይሆን?›› በሚል ርዕስ ባቀረቡት የጥናት ወረቀታቸው እንዲህ ብለው ነበር፡-
… ከኢትዮጵያ ታሪክ የምንገነዘበው አንድ ሐቅ ቢኖር፣ ካንዴም ሁለቴ አለቀላት፣ ፈረሰች ተብሎ ከተደመደመ በኋላ እንደገና እንዴት እንዳሰራራችና አዲስ ሕይወት እንደዘራች ነው፡፡ በአክሱም ዘመን ፍፃሜ፣ በ፲፮ኛው መቶ ዓመት፣ በዘመነ መሳፍንትና በዘመናችንም በአብዮቱ ወቅትና በደርግ ውድቀት ጊዜ የታየው ሁኔታ ይኸው ነው፡፡ ይህ የኢትዮጵያ እንደገና የማንሰራራት ችሎታ ሀገሪቱ በዘመናት የታሪክ ሂደት ያካበተችው ሰብዓዊና ባሕላዊ እሴቶች ውጤት ይመስለኛል፡፡
ፕሮፌሰር ባሕሩ ተስፋዋ የተቆረጠ፣ የጨለመ ነው የተባለችው ኢትዮችጵያችን ከአሁን ወዲያ አበቃላት፣ በቃ፣ ሞተች፣ ተረሳች ስትባል ዳግም ያንሰራራችበት የትንሣኤ/የሕዳሴ ታሪክ ዘመናት እንደነበሯትም ማስታወስ አለብን፡፡ ፕ/ር ባሕሩ መጪው ዘመን ለኢትዮጵያችን የተሻለና ብሩህ ዘመን እንዲሆን የምንመኝ ሁሉ ብሩህ ተስፋን ሰንቀን በአንድነት እጅ ለእጅ በመያያዝ መነሳት እንደሚገባን የሚያሳስበን ምሁራዊ አስተውሎት የታከለበት ትንታኔ ነው በዚህ ጥናታዊ ጽሑፋቸው ያስቀመጡት፡፡
ስለሆነም በዚህች አጭር መጣጥፌ መደምደሚያዬም ይህችን የሁላችንም የሆነች ኢትዮጵያችንን ለመጪው ትውልድ እንደተከበረች፣ እንደታፈረችና እንደተፈራች በክብር ማስተላለፍ አገራችንን እንወዳለን፣ ለወገን እንቆረቆራለን የምንል ኢትዮጵያን ሁሉ ግዴታና ሓላፊነት እንደሆነ ነው የማስበው፡፡
ስለዚህም እንደ አገርም፣ እንደ ሕዝብም ለረጅም ዘመናት በአንድነት አስተሳስሮ ያቆየንን ታሪካዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እሴቶቻችንና ቅርሶቻችንን ጠብቀን፣ ያለፈውን የታሪክ ጠባሳችንን/ቁርሾአችንን በይቅርታ ልብ ሽረን፣ እያመረቀዘ ያስቸገረንን የትናንትና ስብራታችንን፣ ቁስላችንን በፍቅር ዘይት አለስልሰንና አክመን እጅ ለእጅ በመያያዝ- የሰላምና የአንድነት፣ የልማትና የዕድገት ጮራዋ፣ ጸዳሏ የሚደምቅባትን ታላቋን ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ በአንድነት ሆነን በፍቅርና በይቅርታ ልብ ቃል ኪዳናችንን ማደስ እንደሚኖርብን ማስታወስ፣ ማሳሰብ እወዳለኹ፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!!

‹‹ቀራንዮ፣ መድኃኔዓለም፣ ካህናቱ› (በዳንሄል ክብረት)

0
0

ቅዱስ ጳውሎስ ተከስሶ በቂሣርያው ገዥ በፊስጦስ ፊት በቀረበ ጊዜ አይሁድ ለብቻቸውቀርበው በቅዱስ ጳውሎስ ላይ ይፈርድበት ዘንድ ጎትጉተውት፣ እነርሱ ማስረጃ ያሉትንም አቅርበውለት፣ ሕጋቸውንም ጠቅሰው ማሳመኛአቅርበውለት ነበር፡፡ አሕዛባዊው ገዥ ፊስጦስ ግን እግዚአብሔርን እናውቃለንም፣ እንፈራለንም ከሚሉት አይሁድ ተሽሎ ያሉትንከማድረግ ራሱን ከለከለ፡፡
daniel-kibret-300x207
ከጥቂት ቀናት በኋላ ንጉሥ አግሪጳና በርኒቄ ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ ጉዳዩንአቀረበላቸው፡፡ ፊስጦስ አይሁድ ያቀረቡትን ስሞታ፣ ውትወታና ክስ ተቀብሎ በቅዱስ ጳውሎስ ላይ ያልፈረደበትን ምክንያት ለአግሪጳሲገልጥለት ‹‹ተከሳሹ በከሳሾቹ ፊት ለፊት ሳይቆም፣ ለተከሰሰበትም መልስ ይሰጥ ዘንድ ፈንታ ሳያገኝ፣ ማንንም ቢሆን አሳልፎመስጠት የሮማውያን ሥርዓት አይደለም›› ብሎ መሆኑን ነግሮታል (የሐዋ.25÷16)፡፡

ይህ በሮማውያን ዘመን እጅግ የታወቀውን ራስን በእኩል ደረጃ የመከላከል መብትበተመለከተ ሮማዊው ታሪክ ጸሐፊ አፒያን (95-165ዓም) በጻፈው Civil War በተሰኘው መጽሐፉ (3:54) ላይ ‹‹የምክርቤት አባሎች፣ ሕጉ የተከሰሰ ሰው የተከሰሰበትን ሰምቶ በእርሱ ላይ ከመፈረዱ በፊት መልስ የመስጠት መብት አለው ይላል›› ሲልአሥፍሮት ነበር፡፡ ፊሊክስ የጠቀሰው ይኼንን ነው፡፡ አበው በትርጓሜያቸው ‹አሕዛብ ፍርድ ይጠነቅቃሉ›› ሲሉ የመሰከሩት እንዲህያለው የሮማውያንን ሕግ ነው፡፡ ለዚህ ጥንቁቅ የፍርድ ሥርዓትም ሲሉ አያሌ የሮማውያንን የፍተሕና የፍርድ ሐሳቦች በቤተክርስቲያን የፍትሕ ሥርዓት ውስጥ (በቀኖና) እንዲገቡና እንዲሠራባቸው አድርገዋል፡፡

ይህንን የምትተረጉምና የምታስተምርን ቤተ ክርስቲያን እንወክላለን የሚሉ ሰዎች ናቸውሰሞኑን ተሰብስበው ተከሳሹ በሌለበት ፍርድ ሲሰጡ ያየናቸው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ተሳሳተ ተብሎ እንኳን ቢሆን ቤተ ክርስቲያኒቱለአርዮስና ለንስጥሮስ፣ ለመቅዶንዮስና ለሰባልዮስ የሰጠችውን መብት ቤተ ክህነቱ ለማኅበረ ቅዱሳን ሊነፍገው አይገባም ነበር፡፡በቀደዱላቸው ቦይ መንጎድ፣ ተጠልቷል ብለው በሚያስቡት ላይ መፍረድ ሃይማኖታቸው የሆነ፤ ፓትርያርኩን ምን ያስደስታቸዋል እንጂየትኛው እውነት ነው ለሚለው የማይጨነቁ ሰዎች የክስ መዓታቸውን ሲያዘንቡ ማኅበሩ መልስ እንዲሰጥ ዕድል ሊሰጠው ይገባ ነበር፡፡ነገር ግን ሰዎቹ ለበዓሉ የሚስማማውን ቀለም ትተው ለባለ ሥልጣኑ የሚስማማውን ቀለም መረጡ፡፡ ሊቁ ክፍለ ዮሐንስ ‹ካህንከመሆን እረኛ መሆን ይሻላል› እንዳለው ከቤተ ክህነት ፊልክስ ተሽሏል፡፡
ፊሊክስ ለቅዱስ ጳውሎስ፣ ሠለስቱ ምእት ለአርዮስ፣ ማኅበረ ኤፌሶን ለንስጥሮስየሰጡትን ዕድል ቤተ ክህነቱ ለማኅበረ ቅዱሳን ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ ለምን?

ሰዎቹ እውነቱን ለመጋፈጥ ዐቅም አንሷቸዋል ማለት ነው፡፡ የሚሉት ነገር የሆኑአካላትን ስለማስደሰቱ እንጂ እውነት ስለመሆኑ ርግጠኞች አይደሉም፡፡ ስለዚህም ተከራካሪያቸውን ለመስማትና የእነርሱ ‹እውነት›ሲሞገት ለማየት ዐቅም ያንሳቸዋል፡፡ ወይም ደግሞ

ከክርክሩ በፊት ውሳኔውን ወስነው ጨርሰዋል፡፡ ፓትርያርክ አቡነ ቴዎፍሎስን ለደርግአሳልፈው የሰጡት የቤተ ክህነት ሰዎች እንዲህ ነበር ያደረጉት፡፡ ፓትርያርኩን አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ ውሳኔውን ወስነዋል፡፡ነገር ግን ለውሳኔው ምክንያት መፈለግ ነበረባቸው፡፡ ስለዚህም አቡነ ቴዎፍሎስ ሠሩ ያሏቸውን ጥፋቶች ለብቻቸው ተሰብስበው፣‹በደላቸውን› ዘርዝረው፣ እርሳቸው መልስ ሊሰጡ በማይችሉበት ሁኔታ ለደርግ አስተላለፉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ለብቻቸው መሰብሰብየፈለጉት፣ የፓትርያርኩንም መልስ የመስጠት መብት የነፈጉበት አንዱ ምክንያት ፓትርያርኩ በሚሰጡት መልስና በሚያቀርቡት ማስረጃእውነታቸው ነፋስ ያየው ገለባ እንዳይሆንባቸው ነው፡፡ ወይም

እነዚህ ሰዎች የራሳቸውን ሥራ አይደለም እየሠሩ ያሉት፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱን ሲበጠብጡየኖሩት ካህናተ ደብተራ (ከቤተ ክህነት ደመወዝ እየወሰዱ ለቤተ መንግሥት ሲሠሩ የኖሩ ካህናት ነን ባዮች) ዋናው መለያቸውየሚሠሩት የራሳቸውን ሥራ አለመሆኑ ነው፡፡ የመለካዊነት ጠባይ ስላላቸው ሌሎች ተናገሩ የሚሏቸውን ይናገራሉ፣ ፈጽሙልንየሚሏቸውን ይፈጽማሉ፤ አውግዙልን የሚሏቸውን ያወግዛሉ፤ አጽድቁልን የሚሏቸውንም ያጸድቃሉ፡፡ የሚሠሩት ሥራ የላኳቸውን ሰዎችማርካቱን እንጂ የሚያስከትለውን ነገርና የሚያስከፍለውን ዋጋ አያውቁትም፡፡ እነዚህ ነበሩ አባ በጸሎተ ሚካኤልን ያሰደዱት፣እነዚህ ነበሩ አባ ፊልጶስን ያንከራተቱት፣ እነዚህ ነበሩ እጨጌ ዕንባቆምን ለልብነ ድንግል ከስሰው ምንም ባላጠፋው ጥፋት‹ጉንጽ› በተባለው ዓለም በቃኝ እስር ቤት ያሳሠሩት፤ በኋላም ለሀገሪቱ ጥፋትን ያመጡት፡፡ጥይት የመታው ሰው ተናድዶ ‹‹ምነው እንዲህ ታበላሸኝ›› ቢለው ‹‹እባክህ እኔ አይደለሁም፣እኔ ተተኮስኩ እንጂ ተኳሹ ሌላ ነው፤ እኔ መልክተኛ ነኝ›› አለው፡፡ ‹‹ተኳሹ የት አለ?›› ቢለው ‹‹እርሱማ አይታይም ተደብቆነው የሚተኩሰው፤ እርሱ ስለሚደበቅኮ ነው እኔ የመጣሁት›› አለው ይባላል፡፡

ወይም እነዚህ ሰዎች ስንፍናቸውን የሚያሳይባቸውን፣ ድካማቸውን የሚገልጥባቸውን፣ሊያጠፉት ወድደዋል፡፡ ሰውዬው ዶሮውን በጦም አርዶ ለምን አረድከው ቢባል ‹‹እሱ ነው ጠዋት እየተነሣ መንጋቱን የሚያሳብቅብኝ፣አርፌ እንዳልተኛበት፡፡ እርሱ ባይጮህ ኖሮ መንጋቱን ማን ያውቅ ነበር? ተኛህ ብሎስ ማን ይከሰኝ ነበር›› አለ አሉ፡፡ ከመንቃትይልቅ ማንቂያውን ማጥፋት፡፡ የ13ኛው መክዘ የደቡብ ሐዋርያ አቡነ አኖሬዎስ ታላቁ በካህናተ ደብተራ ተከስሶ ወደ ንጉሥ ሰይፈአርእድ የቀረበበት ክስ አስቂኝ ነበር፡፡ ‹‹ከንጉሡ የሚበልጥ ቤተ ክርስቲያን ሠርቷል›› ነበር የተባለው፡፡ ጉዳዩን ሊያጣራየሄደው የጉዳም አለቃ ያገኘው ቤተ ክርስቲያን ግን እንደተባለው አልነበረም፡፡ ነገር ግን ከክሱ ንጹሕ መሆኑ ቅጣቱን አላስቀረለትም፡፡ከገዳሙ ወጥቶ በወለቃ በረሃ እንዲከራተት ሆኗል፡፡ ምናለ ከንጉሡ የሚበልጥ ቤተ ክርስቲያን ቢሠራ? የሚያስመሰግነው እንጂ የሚያስነቅፈውአልነበረም፡፡ ለካህናተ ደብተራ ግን ይኼ ስንፍናቸውን ይገልጠዋል፣ እንደ አውራ ዶሮውም መተኛታቸውን ያሳይባቸዋል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶሱ አሁን መስቀለኛ መንገድ ላይ ቆሟል፡፡ የሚቀርቡት ክሶች ለምን ቀረቡማለት አይቻልም፡፡ ነገር ግን በአይሁድ አደባባይ ፍርድ ሲጓደል፣ እንደ ጲላጦስ ሚስት የሚያስጠነቅቅ ያስፈልጋል፡፡ ገለልተኛአካል አቋቁሞ የተባሉትን ያጣራ፡፡ ራሱ የማኅበሩ አመራር ለተከሰሰበት መልስ ይስጥ፡፡ አሕዛባዊው ፊሊክስ ለቅዱስ ጳውሎስየሰጠውን መብት ሲኖዶሱ ለማኅበሩ መስጠት አለበት፡፡ ተጣርቶ በተገኘው ማስረጃና ምስክር መሠረት ውሳኔ ይሰጥ፡፡ ጥፋተኛውይታረም፤ እውነተኛው ይገለጥ፡፡

በዐፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ቀራንዮ መድኃኔዓለም አለቅነት ተሾመው የሄዱትን አባትካህናቱ አስቸገሯቸው፡፡ ለጥቂት ጊዜ የተላኩበትን ሊሠሩ ሞከሩ ግን አልሆነም፡፡ በመጨረሻም ለንጉሡ እንዲቀይሯቸው አመለከቱ፡፡ንጉሡም ምነው ምን ገጠመህ? ቢሏቸው ‹‹ካህናቱም ካህናቱ፣ ቀራንዮም ቀራንዮ፣ መድኃኔዓለምም መድኃኔዓለም›› አሉ ይባላል፡፡ሰቃይ ተሰቃይና የመስቀያ ቦታ አንድ ሲገናኙ ያ ነው ክፉ ዘመን፡፡
ማኅበሩን እንደ ተቋም፣ እንደ ጽ/ቤትና እንደ ድርጅት ማፍረስ ቀላል ነው፤ እንደአስተሳሰብ፣ እንደ አመለካከት፣ እንደ የአገልግሎት መሥመርና አተያይ ግን ማፍረስ አይቻልም፡፡ ዛሬ ማኅበሩን በማፍረስየሚጀመረው አጥር ንቅነቃ ግን መጨረሻው ሲኖዶሱን በማደንበሽ እንዳይጠናቀቅ ያሰጋል፡፡ ባለቤቱን ካልናቁ ነውና፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ለሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 90 ሺሕ ብር የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

0
0

በእንዳለ ደምስስ
mahibere-kidusan
ማኅበረ ቅዱሳን ለአንጋፋውና የሊቃውንት መፍለቂያ ለሆነው የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 90 ሺሕ ብር የሚያወጡ ኮምፒዩተሮች፤ ፕሪንተሮችና መጻሕፍት ጥቅምት 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ለኮሌጁ ደቀመዛሙርት አገልግሎት እንዲውል ድጋፍ አደረገ፡፡

ማኅበሩ ከኮሌጁ በቀረበለት ጥያቄ መሠረት የኮሌጁን ደቀመዛሙርት እውቀት ለማሳደግ የሚያስችሉ ግምታቸው 90 ሺሕ ብር የሚደርሱ 12 ኮምፒተሮች፤ 2 ፕሪንተሮች፤ እንዲሁም ማኅበረ ቅዱሳን በአማርኛና በኦሮምኛ ቋንቋዎች ያሳተማቸውን 184 መጻሕፍት በኮሌጁ አዳራሽ ርክክብ አድርጓል፡፡

በርክክቡ ሥነ ሥርዓት ላይ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሓላፊና የኮሌጁ ዋና ዲን ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ ማኅበሩ ያደረገውን ድጋፍ አስመልከቶ ሲገልጹ “ኮሌጁ በርካታ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን ያፈራ ነው፡፡ ዛሬም በማፍራት ላይ ቢገኝም በርካታ ችግሮች አሉበት፡፤ በዚህም መሠረት ደቀዛሙርቱ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ሽግግር ጋር ለማገናኘትና ከኢንተርኔት አጠቃቀም አንጻር ያለባቸውን ክፍተት ለመፍታት ለማኅበረ ቅዱሳን ባቀረብነው ጥያቄ መሠረት የኮምፒዩተሮችና የመጻሕፍት ድጋፍ በማድረጉ በመላው የኮሌጁ ማኅበረሰብና ደቀመዛሙርት ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ፡፡ ማኅበሩ እንደ ቤተ ክርስቲያን ልጅነቱ እሰየሠጠ ካለው አገልግሎት አንጻር ወደፊት ተጨማሪ ድጋፎችንም እንደሚያደርግልን ተስፋ አደርጋለሁ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ አቶ ተስፋዬ ቢሆነኝ በበኩላቸው ኮምፒዩተሮችና መጻሕፍቱን ካስረከቡ በኋላ እንደገለጹት “ማኅበሩ ከኮሌጁ በተጠየቀው መሠረት ማድረግ ከሚችለው ውስጥ ትንሹን ነው ያደረገው፡፡ ወደፊትም ኮሌጁ በሚያስፈልገው፤ ማኅበሩ ደግሞ በሚችለው መጠን ድጋፍ ያደርጋል” ብለዋል፡፡

በኮሌጁ ውስጥ ከሚገኙት ሊቃውንት መካከል መምህር ሃይማኖት ኃይለ ማርያም ማኅበሩ ባደረገው ድጋፍ በሰጡት አስተያየት “የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ማድረግ መልካም ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን ልጆች በመሆናቸው የቤተ ክርስቲያንን ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ነው የሰጡት፡፡ ሌሎችም ማኅበሩን አርአያ አድርገው ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባል” በማለት ገልጸዋል፡፡

በኮሌጁ መምህራን የተዘጋጁ መጻሕፍትም ለማኅበረ ቅዱሳን ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት እንዲውሉ በመምህራኑ አቅራቢነት፤ በኮሌጁ ዲን አማካይነት ለማኅበረ ቅዱሳን ተበርክቷል፡:

ምንጭ፦ማህበረ ቅዱሳን

Breaking News: ቴዲ አፍሮ ታስሮ ፍርድ ቤት ቀረበ

0
0

teddy afro
ዝነኛው ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ በፌደራል ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በቀረበበት ክስ ምክንያት ዛሬ ታስሮ ፍርድ ቤት ቀረበ፡፡ ድምፃዊው የቀረበበት ክስ ከስምንት ዓመት በፊት ከቀረጥ ነፃ ወደ ሃገር ውስጥ የገባችን ቢኤምደብሊው መኪና ገዝቶ ተገቢውን የቀረጥ ክፍያ ሳያጠናቅቅ ወደ ስሙ አዛውሯል የሚል መሆኑን የኢትዮጲካሊንክ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

ድምፃዊው በዚሁ ክስ መሰረት ዛሬ ረፋድ በአራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ ክሱ ከታየ በኋላ ቀርቦ የዕለቱ ዳኛ 30 ሺህ ብር በማስያዝ በዋስ እንዲፈታ ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜም የዋስ ሂደቱን ለመጨረስና ድምፃዊውን ለማስፈታት የቢሮ ሥራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ታውቋል፡፡

ለቴዲ አፍሮ መከሰስ ምክንያት የሆነችው ይህች መኪና ከዚህ ቀደም በተቀጣበት የሰው ገጭቶ ህይወት ማጥፋት ወንጀል የተከሰሰባት ነበረች፡፡

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live