Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

በተከሰሱ መፅሄቶች ላይ ውሳኔ ለመስጠት ፍ/ቤት ኦሪጂናል መፅሄቶች እንዲቀርቡለት አዘዘ

$
0
0

AddisAdmas በ“አዲስ ጉዳይ”፣ በ“ሎሚ” እና በ“ፋክት” መፅሄት አሳታሚዎችና ሥራ አስኪጆች ላይ ለተመሰረቱት የወንጀል ክሶች የቀረቡት ማስረጃዎች ከየመፅሄቶቹ ገፆች የተቆራረጡና ኮፒ የተደረጉ መሆናቸውን የጠቆመው ፍ/ቤት፤ አቃቤ ህግ ኦርጂናል መፅሄቶችን በማስረጃነት እንዲያቀርብ ትዕዛዝ በማስተላለፍ ለፍርድ ውሳኔ በድጋሚ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ፡፡ ፍ/ቤቱ ከትላንት በስቲያ በዋለው ችሎት አቃቤ ህግ ከጥቅምት 3 በፊት ኦሪጂናል መፅሄቶችን በማስረጃነት እንዲያቀርብ አዟል፡፡

የ“አዲስ ጉዳይ” መፅሄት አሳታሚ ሮዝ አሳታሚና ስራ አስኪያጁ አቶ እንዳልካቸው ተስፋዬ፣ የ“ሎሚ” መፅሄት አሳታሚ ዳዲሞስ ኢንተርቴይመንትና ፕሬስ ስራዎችና ስራ አስኪያጁ አቶ ግዛው ታዬ እንዲሁም የ“ፋክት” መፅሄት አሳታሚ ኢንተርቴይመንትና የፕሬስ ስራዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበርና ስራ አስኪያጅ ፋጡማ ኑርዬ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸው ባለመቅረባቸው ጉዳያቸው በሌሉበት እየታየ ሲሆን በተለያዩ ጊዜያት ታትመው በወጡ መፅሄቶቻቸው ሃሰተኛ ወሬዎች በማውራት፣ ለአመፅ የሚያነሳሱ ፅሁፎችን ለህዝብ በማድረስ፣ በህገ መንግስቱና በህገ መንግስታዊ ስርአቱ ላይ አመፅ ለማስነሳት ሞክረዋል የሚሉ ክሶች እንደቀረበባቸው ይታወሳል፡፡ ከ“ፋክት” መፅሄት አሳታሚ ድርጅት ስራ አስኪያጅ በስተቀር የሁሉም ተከሳሽ መፅሄቶች ሥራ አስኪያጆችና ባለቤቶች አገር ለቀው መውጣታቸው ይታወቃል፡፡


በጋምቤላ ግጭት የተጠረጠሩ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው

$
0
0

ሸፍተው የነበሩ የዞኑ የፖሊስ ልዩ ሃይል አዛዥና የሚሊሽያ አባላት እጃቸውን ሰጡ

militaryበጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በጎደሬ ወረዳ፣ በመዠንገር ዞን በተቀሰቀሰውና አሁንም ድረስ በአንዳንድ ቦታዎች በቀጠለው ግጭት እጃቸው እንዳለበት የተጠረጠሩ የክልሉ ባለስልጣናት ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው፡፡ በአዲስ አመት ዋዜማ የተቀሰቀሰውና ከ40 በላይ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈው ግጭት መነሻ ከመሬት ባለቤትነት ጋር የተያያዘ እንደሆነ ለአዲስ አድማስ የገለፁት ምንጮች፤ “ደገኞች መሬታችንን ይልቀቁ” የሚሉ የአካባቢው ተወላጆችና አንዳንድ የክልሉ ባለስልጣናት በመንግስት ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን የሰፈራ ፕሮግራም ተገን በማድረግ ነባር ይዞታ ያላቸውን ነዋሪዎች በማፈናቀላቸው ግጭቱ መፈጠሩን ተናግረዋል፡፡

በአካባቢው ተወላጆችና ከሌሎች አካባቢዎች በመጡ ነዋሪዎች መካከል ለረጅም ጊዜ የቆየና በየጊዜው የሚያገረሽ ግጭት እንዳለ የሚታወቅ ሲሆን፣ በቅርቡ የተከሰተው ግጭት ሊቀሰቀስ እንደሚችል የፌደራል መንግስት በደረሰው መረጃ መሰረት፣ በአፈ ጉባኤ ካሳ ተክለብርሀን የተመራ ቡድን ከክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በመተባበር በአካባቢው የማረጋጋት ስራ ቢሰራም፣ በዞኑ ያሉ አንዳንድ የፖሊስና የሚሊሺያ አባላት “መሬታችንን ይልቀቁ” የሚለው ሃሳብ እንዲሰርፅ በማድረጋቸው ግጭቱ እንደተፈጠረ ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡

ግጭቱ ከተፈጠረ በኋላም የዞኑን የፖሊስ ልዩ ሀይል አዛዥ ጨምሮ የፖሊስና የሚሊሽያ አባላት ሸፍተው ጫካ መግባታቸውን የተናገሩት ምንጮች፤ በአሁኑ ወቅት አዛዡና ሌሎች ጥቂት አባላት እጃቸውን ለመንግስት ሃይሎች እንደሰጡ ገልፀዋል፡፡ በአካባቢው የተከሰተው ግጭት ሁነኛ መፍትሔ ካልተበጀለት፣ በአቅራቢያ ወደሚገኙ ሌሎች አካባቢዎች ሊዛመት ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት መፈጠሩን ያመለከቱት ምንጮቹ፤ ከወራት በፊት ማንነታቸው ያልታወቀ የታጠቁ ሰዎች ዲማ ተብሎ በሚጠራው የክልሉ አካባቢ አስር ሰላማዊ ዜጎችን ገድለው መሰወራቸውን ገልፀዋል፡፡ በአካባቢው የተከሰተው ግጭት ከክልሉ የፀጥታ ሃይሎች ቁጥጥር በላይ በመሆኑ፣ የፌደራል ፖሊስና የመከላከያ ሃይል ጣልቃ ገብቶ የማረጋጋት ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡

አዲስ አድማስ

የዓለም ባንክ ኢትዮጵያ ለብድር ዕዳ አደጋዎች የመጋለጥ ዕድሏ እየሰፋ ነው አለ

$
0
0

ሰሞኑን ለሦስት ቀናት ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩት የዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተርና የኦፕሬሽን ዋና ኃላፊ ስሪ ሙሊያኒ ኢንድራዋቲ፣ እያደገ የመጣው የብድር ዕዳ መጠን በኢትዮጵያ ላይ አደጋዎችን ሊያስከትል እንደሚችል ገለጹ፡፡

የዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተርና የኦፕሬሽን ዋና ኃላፊ ስሪ ሙሊያኒ ኢንድራዋቲ

የዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተርና የኦፕሬሽን ዋና ኃላፊ ስሪ ሙሊያኒ ኢንድራዋቲ

ኢንድራዋቲ ባለፈው ረቡዕ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ ምንም እንኳን የአገሪቱ የብድር ዕዳ መጠን ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት አኳያ ያለው ድርሻ አነስተኛ ቢሆንም፣ የዕዳውን መጠን በግልጽነት ለማስተዳደር የሚችልና ግልጽነት የሰፈነበት አስተዳደር ማስፈን የመንግሥት ግዴታ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አገሪቱ ያለባት ጠቅላላ የብድር መጠን 20 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል፡፡ ከዚህ ውስጥ 12 ቢሊዮን ዶላር ከውጭ ምንጮች የተገኙ ብድሮችን የሚሸፍን የዕዳ መጠን ነው፡፡ በዚህ መሠረት ከጠቅላላ አገር ውስጥ ምርት አኳያ የዕዳው ድርሻ 44 ከመቶ መድረሱን ይጠቁማል፡፡

ኢንድራዋቲ እንደሚገልጹት፣ ይህ አኃዝ ዝቅተኛ በሚባለው የዕዳ ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ነገር ግን የመንግሥት የኢንቨስትመንት ወጪዎች እየተበራከቱ በመምጣታቸው ምክንያት የዕዳ መጠኑን በዚያው ልክ እያደገ በመሆኑ፣ የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን በሚመለከት ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝና ከሚመለከታቸው ሚኒስትሮች ጋር መነጋገራቸውን አስረድተዋል፡፡ ከውይይቶቹ መካከልም በመንግሥት አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርሞች ላይ ያተኮረው አንዱ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በዚህም መንግሥት በአስተዳደራዊ መዋቅሮቹ ላይ ማሻሻያ በማድረግ፣ ግልጽነትና ኢኮኖሚውን በብቃት የማስተዳደር ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

የመንግሥት የልማት ድርጅቶች በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን  የኢንቨስትመንት ወጪን መነሻ በማድረግ፣ በኢትዮጵያ እየጨመረ የሚገኘውን የብድር ዕዳ መጠንና ሊከሰት የሚችለውን አደጋ ለመቋቋም የሚያስችል አሠራር ማምጣት እንደሚገባቸው መክረዋል፡፡

‹‹ይህንን ለማከናወን አስተማማኝ የፋናይናንስ ሪፖርት ያስፈልጋል፡፡ ግልጽነትና ወጥነት በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ ተዓማኒነት ያለው መረጃ መኖሩ ግድ ይላል፡፡ አሁን እየታየ ያለው የብድር ሁኔታ በኢትዮጵያ ላይ ተጨማሪ የተጋላጭነት አደጋ ማስከተሉ በእርግጠኝነት የማይቀር ነው፤›› ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የብድር ዕዳዋን ለማቃለል የወጪ ንግድ ሚዛኗ ወሳኝ መሆኑን ኢንድራዋቲ ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ባለፉት ሦስት ዓመታት በወጪ ንግድ መስክ አገሪቱ ዝቅተኛ ውጤት ስታዝመገዘብ መቆየቷ ለብድር ዕዳ ያላትን ተጋላጭነት አስፍቶታል ይባላል፡፡

አገሪቱ ስታዝመግብ የቆየችው የኢኮኖሚ ዕድገት መልካም የሚባል መሆኑን የጠቀሱት ኢንድራዋቲ፣ ይህም ሆኖ ኢኮኖሚው መዋቅራዊ ለውጥ ለማምጣት ብዙ እንደሚቀረው ገልጸዋል፡፡ የኢኮኖሚው ዕድገት በርካታ የሥራ መስኮችን ሊፈጥሩ የሚችሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ለማምጣት ብዙ መንገድ ይቀረዋል ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ፣ ባንኩ የኢንዲስትሪ ዞኖች ግንባታን ፋይናንስ እያደረገ እንደሚገኝም አስታውሰዋል፡፡ በአዲስ አበባ ቦሌ ለሚ ሁለተኛ ምዕራፍና በአቃቂ ቃሊቲ ቂልንጦ አካባቢ ለሚገነቡ ሁለት የኢንዱስትሪ ዞኖች የሚውል የ250 ሚሊዮን ዶላር ብድር መፍቀዱን፣ በኢትዮጵያ የባንኩ ዳይሬክተር ጉዋንግ ዚ ቼን ገልጸዋል፡፡

ባንኩ ለመሠረተ ልማት ከሚሰጠው ድጋፍ በተጨማሪ በኢትዮጵያ ለመሠረታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራምም ድጋፍ ያደርጋል፡፡ ተዘዋውረው በጎበኟቸው የሴፍቲኔት ጣቢያዎች ጥሩ ውጤት እንዳዩ ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ተናግረው፣ እየጨመረ በመጣው የከተሞች የምግብ እጥረት ተጋላጭነት ሳቢያ በድምሩ አሥር ሚሊዮን ሰዎች በሴፍቲኔት ፕሮግራም ይታቀፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ይፋ አድርገዋል፡፡

ስሪ ሙልያኒ ኢንድራዋቲ የዓለም ባንክን ከመቀላቀላቸው አስቀድሞ የኢንዶኔዥያ የፋይናንስ ሚኒስትር በመሆን አገልግለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የኢኮኖሚ ጉዳዮች አስተባባሪ ሚኒስትር በመሆንም ሠርተዋል፡፡ እ.ኤ.አ. በ2010 የዓለም ባንክን የተቀላቀሉት ኢንድራዋቲ፣ በምክትል ፕሬዚዳንትነት ደረጃ የሚመሯቸው በርካታ መስኮች አሉ፡፡ በማኔጂንግ ዳይሬክተርነት ሥልጣናቸው የባንኩን የአካባቢያዊ ሥራዎች በጠቅላላ የመምራት ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል፡፡

ወያኔ ከነዋይ ደበበ ጋር በስዊድን ያዘጋጀው የሙዚቃ ኮንሰርት በኪሳራ ተመታ፤ በጀርመንም ይቀጥላል

$
0
0

በሃገረ ስዊድን በትናንትናው ዕለት ወያኔ ነዋይ ደበበን ተጋባዥ ድምፃዊ አድርጎ ያዘጋጀው የሙዚቃ ምሽት በታዳሚ እጦት ተመታ። ነዋይ ደበበ ከፍተኛ የሞራል ድቀት እንደደረሰበትም ጉዳዩን በቅርብ ይከታትሉ የነበሩ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ዘግበዋል። ነዋይ በጀርመንም እንዲሁ ኦክቶበር 4 ከፍተኛ ቦይኮት እንደሚገጥመው በዛው ያሉ ኢትዮጵያውያን አስታውቀዋል።
ወያኔ ከነዋይ ደበበ ጋር በስዊድን ያዘጋጀው የሙዚቃ ኮንሰርት በኪሳራ ተመታ፤ በጀርመንም ይቀጥላል
በውጭ ሃገር የሕወሓት መንግስትን እየደገፉ በሙዚቃ ኮንሰርትና በሌሎች የትያትር ዝግጅቶች ገንዘብ ለመሰብሰብ የሚመጡ አርቲስቶችን ሕዝቡ ቦይኮት እየጠራባቸው ሲህን ከዚህ ቀደም በጀርመን ማዲንጎ አፈወርቅ በተመልካች ድርቅ ተመቶ ወደ ሃገር ቤት ተመልሷል። ሃመልማል አባተም በዋሽንግተን ዲሲ ለሲዲ ምርቃት ያዘጋጀችው ኮንሰርትም እንዲሁ በተመልካች ድርቅ የተመታ ሲሆን፤ ሸዋፈራው ደሳለኝ በበኩሉ በደረሰበት ከፍተኛ ተቃውሞ የኮሚዲ ዝግጅቱን ሳያቀርብ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል።

“ነዋይን ነዋይ አሳሳተው” በሚል በተደጋጋሚ የሚተቸው ድምጻዊው በስዊድን የሕወሓት አስተዳደር በጠራው ኮንሰርት ላይ እንደሚገኝ ፍላየር ከተበተነ ጊዜ ጀምሮ በዚያው ሃገር የሚገኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በመሰባሰብ የቦይኮት ፍላየሮችን በማዘጋጀት ሲቀስቀሱ ሰንብተዋል። በዚህም መሠረት ነዋይ ትናንት ምሽት የሕዝቡን ተቃውሞ በመፍራት ተደብቆ በመግባት ዝግጅቱን ያቀረበ ሲሆን መድረክ ላይ ሲወጣ የጠበቀው የሕዝብ ቁጥር ከ50 የማይበልጥ በመሆኑ እጅጉን ማፈሩን አብረውት የነበሩ የቅርብ ምንጮች ገልጸውልናል። በዚህ ኮንሰርት ላይ የተገኙት 50 የማይሞሉት ሰዎችም የኢምባሲ ሰራተኞች እና አንዳንድ ከኢትዮጵያ መንግስጥ ጥቅማትቅም የሚያገኙ ሶማሌዎች እንደሆኑ ምንጮቻችን ገልጸዋል። እንደነዚሁ የቅርብ ምንጮች ገለጻ ነዋይ በኮንሰርቱ ውስጥ የተጠበቀውን ያህል ሰው ባለመገኘቱ “ሕዝቡን ምን አድርገነው ነው፤ ስንጠራው የማይመጣው?” እስከማለት ደርሷል። ነዋይ በተደጋጋሚ በሆዱ ሳይሆን በሕሊናው እንዲያስብ ተመክሯል የሚሉት በስዊዲን የሚገኙት ኢትዮጵያውያን “ሕዝቡን ምን አድርገነው ነው ስንጠራው የማይመጣው?” ማለቱ በራሱ የአመለካከት ደረጃው የት ላይ እንዳለ ያሳያል ብለዋል።

በተመሳሳይ ዜና ነዋይ ደበበ በጀርመን ሃገር ኦክቶበር 4 የሙዚቃ ዝግጅት እንደሚያቀርብ የሰሙት ኢትዮጵያውያን ቦይኮት ለማድረግ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረጉ እንደሚገኙ ጨምሮ የደረሰን ዜና ያስረዳል።

ነዋይ ደበበ በቅርብ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ የመጣ ጊዜ ለመለስ ዜናዊ የዘፈነውን “የሙሴ በትር” ዘፈን ‘ዝፈን ብለው ሰጥተውኝ እንጂ ትርጉሙ አልገባኝም ነበር፤ ከዘፈንኩት በኋላ ነው መሳሳቴን ያወቅኩት” ብሎ ለጓደኞቹ የነገራቸው ሲሆን ወዲያው ወደ አዲስ አበባ ሲመለስ ደግሞ ተገልብጦ በተቃራኒው መገኘቱን የቅርብ ሙያ አጋሮቹ ይተቹታል።

ነዋይ የስዊድን ኮንሰርቱ ከመደረጉ በፊት በኢሳት ራድዮ ተቦርነ ያቀረበውን ዜና ለግንዛቤ እዚህ አምጥተነዋል፦

Health: ገንዘብህ ያገልግልህ እንጂ አታገልግለው

$
0
0

ከሊሊ ሞገስ

ድሃ ሀብታም፣ ነጭ ጥቁር፣ አጭር ረጅም፣ ሴት ወንድ፣ ህጻን አዋቂ ሁሉም በዚህች ምድር የህይወት ምህዋር ውስጥ የሚመርመሰመሱ ተዋንያን ሲሆኑ ህይወት ደግሞ በራሷ መድረክ ናት፡፡ እኒህ ሁሉ ፍጡራን በዚህች የህይወት መድረክ ላይ የተለያየ ህይወትን ይመራሉ፡፡ አንዳንዶች ህይወት በራሷ እየገፋቻቸው ለመውደቅ ሲፍገመገሙ ሌሎች ደግሞ ግፊያውን ተቋቁመውና ከግፊያው ተምረው ስኬታማ ይሆናሉ፡፡ አንድ ነገር እርግጠኛ ሁን፡፡ ዩኒቨርሲቲ ገብተህ ዲግሪና ፒኤችዲ መያዝህ በገንዘብ በኩል ያለህ ጡንቻ የበረታ እንዲሆን አያስችልህም፡፡ ምክንያቱም የገንዘብ ማግኛ ምስጢሩን ት/ቤት ውስጥ አልተማርከውም፡፡ ብዙ ቱጃሮችን እስኪ ተመልከት! ብዙዎች ሰርተፍኬት እንኳ የላቸውም፡፡ ይኸውልህ ምስጢሩ ያለው ከሀብታሙና ድሃው አባትህ ላይ ነው፡፡ ድሃው አባትህ የተማሩ ሲሆን አሁን ድረስ ግን ለገንዘብ ሲል ይለፋል ይደክማል፡፡ ሀብታም አባትህ ግን ባይማርም ስለገንዘብ ያለው እውቀት ላቅ ያለ ነው፡፡ ሮበርት ኪዬሳኪ ዛሬም የሀብታሙን አባቱን ባህርይ ይተርከዋል፡፡ እኔ እንዲህ አስማምቼ አቀናብሬዋለሁ፡፡

money‹‹እናንተ ሁለቱ ህፃናት ስለገንዘብ ማግኛ ዘዴ እንዳስተምራችሁ ስትጠይቁኝ የመጀመሪያዎች ናችሁ፡፡ ከ150 ሠራተኞች በላይ ቢኖሩኝም አንዳቸውም ግን ስለገንዘብ ስላለኝ እውቀት ጠይቀውኝ አያውቁም፡፡ በመሆኑም ብዙዎች ወርቃማ ጊዜያቸውን ገንዘብ ለማግኘት ሲባክኑ ያሳልፉታል፡፡ የሚሰሩትን ነገር በምንም ተአምር አይረዱትም፡፡ በመሆኑም ማይክ አንተ ከእኔ ገንዘብ እንዴት እንደሚገኝ ልትማር እንደምትፈልግ ሲነግረኝ አንድ ከእውነተኛው ህይወት ጋር የተያያዘ ኮርስ ዲዛይን ለማድረግ ወሰንኩ፡፡ ፊቴ ሰማያዊ እስኪሆን ማውራት እችላለሁ፡፡ ነገር ግን የምትሰሙት ነገር አይኖርም ነበር፡፡ በመሆኑም ህይወት በራሷ ጊዜ እንድትገፋችሁ አደረኩ ያኔ ትሰሙኛላችሁ፡፡ ለዚያ ነው 10 ሣንቲም ብቻ የከፈልኳችሁ›› ‹‹ታዲያ ትከፍለን ከነበረው አስር ሣንቲም የተማርኩት ነገር ምንድነው? በቃ በርካሽ እያሰራህ የሠራተኞችህን ጉልበት መበዝበዝ ነው?›› ስል ጠየኩ፡፡ ሀብታሙ አባቴ ወንበሩን ወደኋላ ተደግፎ ከልቡ ከሳቀ በኋላ ንግግሩን ቀጠለ፡፡ ‹‹አመለካከትህን ብትቀይር የተሻለ ነው፡፡ እኔን መውቀስህንና የችግሩ ምክንያት መሆኔን ማሰብህን አቁም፡፡ የችግሩ ምንጭ እኔ እንደሆንኩ ካመንክ እኔን ልትቀይረኝ ይገባል፡፡ ነገር ግን ችግሩ ያልተ እንደሆነ ከተገነዘብክ ራስክን ትለውጣለህ፡፡ አንድ ነገር ተማርና ራስክን ሀብታም አድርግ፡፡ ብዙ ሰዎች ሌሎች ሰዎችን ራሳቸውን እንዲለውጡ ይፈልጋሉ፡፡ አንድ ነገር ልንገርህ፤ ከሌሎች ሰዎች ይልቅ አንተን ራስክን መለወጥ ይቀልሃል›› አለ ሀብታሙ አባቴ፡፡ ‹‹አልገባኝም›› ስል ጠየኩ፡፡ ‹‹ለአንተ ችግር እኔን አትውቀሰኝ›› ሲል መለሰ፡፡ ‹‹ነገር ግን 10 ሣንቲም ብቻ ከፍለኸኛል ስጠይቀው መለሰና ‹‹ታዲያ ምን ተማርክ?›› ሲል ሀብታሙ አባቴ እየሳቀ ጠየቀኝ፡፡

‹‹በቃ በርካሽ ታሰራለህ›› ሲል መለስኩለት፡፡ ሀብታ አባቴ ቀጠለና ‹‹አየህ አሁንም ችግሩ እኔ እንደሆንኩ ታስባለህ፡፡ ነገር ግን ችግሩ ያንተ ነው፡፡ በቃ ይህን አመለካከትክን ግፋበት፤ ነገር ግን የምትማረው ነገር አይኖርም፡፡ እኔ ችግሩ እንደሆንክ አሁንም አመለካከትክን ቀጥል! ግን ምን ምርጫ አለህ?›› ሲል ጠየቀኝ፡፡ ‹‹ማለት ጥሩ ክፍያ ካልከፈልከኝ ወይም ክብር ካልሰጠኸኝ ስራዬን እለቃለሁ›› አልኩት፡፡

‹‹ጥሩ ድምዳሜ ነው፡፡ ይህንማ ብዙዎች ያደርጉታል፡፡ ስራቸውን ለቀው በመሄድ የተሻለ አጋጣሚ፣ ከፍተኛ ክፍያ በማግኘት ችግራቸውን የሚያቃልሉ ይመስላቸዋል፡፡ ነገር ግን አይሰራም፡፡ ‹‹ታዲያ ችግሩን ምን ይፈታዋል?›› ይችን በሰዓት አስር ሣንቲም እየወሰድኩ?›› ስል ጠየኩት፡፡ ፈገግ እያለ ‹‹ያን ሌሎችም ያደርጉታል፡፡ ያን ክፍያ እየተቀበሉ ቤተሰባቸውን ግን በገንዘብ እጥረት እንደሚሰቃዩ ያውቃሉ፡፡ ነገር ግን የሚያደርጉት ያ ብቻ ነበር፡፡ በቃ የገንዘብ መጨመርንና ያ ብር ችግሩን ይፈታዋል ብለው ያስባሉ፡፡ አንዳንዶች ይህን ሲቀበሉ ሌሎች ስራ በመቀየር ጠንክረው ይሰራሉ ግን አሁንም አነስተኛ ብር ይቀበላሉ፡፡

መሬት መሬቱን እያየሁ ሀብታሙ አባቴ ያለኝን ነገር መረዳት ጀመርኩ፡፡ ያለው ነገር የህይወት ፈተናዋ እንደሆነ እየተረዳሁት መጣሁ፡፡

ብሩህ በሆነው ቅዳሜ ጠዋት ከድሃው አባቴ ሙሉ በሙሉ ፍፁም የተለየ አመለካከት (Point of view) እየተማርኩ ነበር፡፡ ገና በ9 ዓመቴ ሁለቱም አባቴ እኔ እንድማር እንደሚፈለጉ እያወኩ አደኩ፡፡ ሁለቱም አባቴ እንድማር ያበረታቱኛል፡፡ ነገር ግን ተመሳሳይ የሆነ ነገር አያስተምሩኝም፡፡

ያ ድሃው አባቴ በቃ ልክ እርሱ የሰራውን እሰራ ሁሉ ዘንድ ይመክረኛል፡፡ ‹‹ልጄ ጠንክረህ እንድታጠና እፈልጋለሁ፤ ጥሩ ውጤት (grade) ማግኘት ይኖርብሃል በመሆኑም አስተማማኝ (Secure) የሆነ ስራ በአንድ ትልቅ ካምፓኒ ውስጥ ታገኛለህ፡፡ የተለያየ ጥቅማጥቅምም እንደምታገኝ እርግጠኛ ሁን ይለኛል፡፡ ሀብታሙ አባቴ ግን ከዚህ በተለየ ገንዘብ እንዴት እንደማገኝና እንዴትስ ለእኔ ሠራተኛ እንዲሆን ማድረግ እንደምችል እንድማር ይፈልጋል፡፡ ይህን ትምህርት ያገኘሁት ክላስ ውስጥ በተሰጠ ትምህርት አልነበረም፡፡

ሀብታሙ ሀባቴ አሁንም ትምህርቱን ቀጥሏል፡፡ ‹‹በሰዓት አስር ሣንቲም በመስራታችሁና በመናደዳችሁ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡ ባትናደዱና እንዲሁ ብትቀበሉት ኖሮ ላስተምራችሁ እንደማልችል በነገርኳችሁ ነበር፡፡ ልብ በሉ እውነተኛ ትምህርት ሃይልን ይፈልጋል፣ መከራን መቀበልና ከፍተኛ የሆነ ፍላጎትን ይጠይቃል፡፡ ንዴት የዚያ ክፍል ዋና ቀመር (formula) ነው፤ ስቃይ ፍቅርና ንዴት የተደባለቀበት ነው፡፡ ይህ ሁኔታ ወደ ገንዘብ ሲመጣ ብዙ ሰዎች በጥንቃቄና በአስተማማኝ ሁኔታ ጨዋታውን ለመጫወት ይፈልጋሉ፡፡ ያለህ ጥንካሬ ደግሞ እኒህን ነገር ሊመራቸው አይችልም ፍርሃት እንጂ፡፡

ለዚያ ነው በዝቅተኛ ክፍያ ስራ ሊሰሩ የሚስማሙት? ስል ጠየቀኩ፡፡ አዎ አለ ሀብታ አባቴ፡፡ ብዙ ሰዎች የሰዎችን ጉልበት እንደበዘበዙ ይናገራሉ፡፡ ምክንያቱን ሲጠየቁ ደግሞ አነስተኛ ክፍያ እየፈከሏቸው እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን እንደ እኔ ከሆነ ጉልበታቸውን የሚበዘብዙት ራሳቸው ሠራተኞች ናቸው፡፡ ያ ደግሞ የእኔ ሳይሆን የእነርሱ ፍራቻ ነው፡፡

‹‹ነገር ግን ጥሩ ክፍያ ልትከፍላቸው እንደሚገባህ አይሰማህም?›› ስል ጠየኩት ‹‹በፍፁም አይሰማኝም፡፡ ይኸውልህ በተጨማሪም ብዙ ገንዘብ ችግርን ሊፈታ አይችልም፡፡ እስኪ የአንተን አባት ተመልከተው፡፡ ብዛት ያለው ገንዘብ እያገኘ ያለውን ቢል እንኳ መክፈል አልቻለም፡፡ ብዙ ሰዎች ብዙ ብር የሚሰጡት ትልቅ እዳ ውስጥ እንዲገቡ ነው፡፡ ‹‹ለዚያ ነው አስር ሣንቲም በሰዓት መከፈሉ›› አልኩና ጠየኩት፡፡ ሀብታሙ አባቴም ‹‹ይህም የምትምህርቱ አንድ አካል ነው›› አለኝ፡፡

‹‹ትክክል ነው!›› አልኩና በድጋሚ ሳኩኝ፡፡ ሀብታሙ አባቴ ግን ንግግሩን ቀጠለ፡- ‹‹አየህ አባትህ ት/ቤት በመግባት በጣም አስፈላጊ ትምህርት ወስዷል፡፡ በመሆኑም የከፍተኛ ደመወዝ ተከፋይ ነው፡፡ ይህም ክፍያ የሰራበት ነው፡፡ አሁን ድረስ ግን የገንዘብ ችግር አለበት፣ ምክንያቱም ት/ቤት ውስጥ እንደነበር ስለገንዘብ ምንም የተማረው ነገር የለም፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ለገንዘብ መስራት እንደሚገባ ያምናል፡፡ እኔም ቀጥዬ ‹‹አንተስ በዚህ ነገር አታምንም?›› ጠየኩት፡፡ ‹‹በፍፁም›› መለሰ ሀብታሙ አባቴ፡፡ ‹‹ለገንዘብ እንዴት መስራት እንዳለብህ ለመማር የምትፈልግ ከሆነ በቃ ሂድና ት/ቤት ቆይ›› ‹‹ታዲያ ብዙዎች ያን ለመማር አይፈልጉም ነበር?›› ስል አሁንም ጠየኩት፡፡ ‹‹አይችሉም፡፡ ምክንያቱም ለገንዘብ እንዴት መስራት እንዳለብህ ለመማር በጣም ቀላል ነው፡፡ በተለይ ስለ ገንዘብ መወራት ሲጀመር ፍራቻ የአንተ መለያ ከሆነ፡፡ ‹‹አልገባኝም›› ስል ግራ ተጋብቼ ጠየኩት፡፡

‹‹ስለሱ ለአሁን ብዙ አትጨነቅ፡፡ አሁን ግን ብዙ ሰዎችን በስራቸው ላይ ተጣብቀው እንዲሰሩ የሚያደርጋቸው ፍራቻ መሆኑን እወቅ፡፡ የቤታቸውን ቢል ያለመክፈል ፍራቻ አለባቸው፡፡ አንዳንዶች ደግሞ አይኖረኝ ይሆናል ብለው ይፈራሉ፡፡ ይህ ደግሞ ለአንድ ፕሮፌሽን ወይም ንግድ መማር ለገንዘብ በመስራት የሚገኝ ክፍያ ነው፡፡ ብዙዎች በራሳቸው ጊዜ ለገንዘብ ባርያ ይሆኑና ሲናደዱ በአለቃቸው ላይ መጮህ ይጀምራሉ፡፡

‹‹ገንዘብ እንዴት ማግኘት እንደሚቻል አንተ ጋር የሚሰጠው ትምህርት የተለየ ነው!›› ስል አስተያቴን ሰነዘርኩ፡፡ ‹‹በትክክል›› ሲል ሀብታሙ አባቴ መለሰልኝ፡፡

ሁለታችንም በዚያ የሚያምር የቅዳሜ የጠዋት ፀሐይ ላይ ፀጥ ብለን ተቀመጥን፡፡ ትንንሽ ጓደኞቼ የቤዝኾል ሊግ ጨዋታቸውን ጀምረዋል፡፡ እኔ ግን በተለያየ ምክንያት በሰዓት አስር ሣንቲም እየተከፈለኝ ለመስራት ወስኛለሁ፡፡ ለዚህም ምስጋናዬ ትልቅ ነው፡፡ አሁን ጓደኞቼ ት/ቤት የማያገኙትን ትምህርት ልማር እንደሆነ ይሰማኛል፡፡

‹‹ለመማር ዝግጁ?›› ሲል ሀብታሙ አባቴ ጠየቀ፡፡ እያስተማርኳችሁ ነበር፡፡ በዘጠን ዓመታችሁ ለገንዘብ ብሎ መስራት የሚፈጥረውን ስሜት አጣጥማችሁ አይታችኋል፡፡ ይህን ዘጠን ዓመትህን በአምሳ ዓመት አባዛውና እዚያ ቦታ ላይ ያሉ ሰዎች የሚሰማቸውን ስሜት አስብ፡፡

‹‹አልተረዳውህም›› አልኩና መለስኩ፡፡ ‹‹ቅድም እኔን ለማግኘት ቁጭ ብለህ ስትጠብቅ ምን ተሰማህ?›› አንደኛው ዕድገትንና ሁለተኛው ደግሞ ከፍተኛ ክፍያ ለማግኘት ስትፈልግ? ‹‹በጣም ንዴት››… አልኩና መለስኩለት፡፡ ሀብታሙ አባቴ ቀጠል አደረገና ‹‹አንተም እንደ ብዙዎች ለገንዘብ ስትል መስራትን ብትመርጥ ኖሮ ህይወትህ ያን ነበር የሚመስለው፡፡

‹‹እሺ ወ/ሮ ማርቲን በሶስት ሰዓት ውስጥ 30 ሣንቲም እጅህ ላይ ስታስቀምጥልህ ምን ተሰማህ?›› ሲል እንደገና ጠየቀኝ፡፡ ‹‹በቂ እንዳልሆነ ተሰማኝ፤ ምንም ነገር አልነበረም፡፡ በጣም ግራ ተጋብቼ ነበር›› ስል መለስኩለት፡፡ ‹‹በቃ ብዙዎች ሰራተኞች የሚሰማቸው ስሜት እንዲህ ነው፡፡ በተለይ የታክስና የሌሎች ነገሮች ተቆረጦ ከተነሳባቸው በኋላ፡፡ አንተ ግን ግፋ ቢል 100% አግኝተሃል›› ሲል መለሰልኝ፡፡

‹‹ማለት ሁሉም ሠራተኞች ደመወዛቸውን ሙሉ በሙሉ አያገኙም ማለት ነው?›› ስል ጠየኩ፡፡

‹‹ማን ያውቃል?›› መንግሥትም ቢሆን በመጀመሪያ የራሱን ድርሻ ያነሳል፡፡ ‹‹እንዴት አድርጎ ይሰራዋል?›› ሲል ደግሜ ጠየኩት፡፡ ‹‹በታክስ ነዋ! ስታገኝ! ስታጠፋ፣ ስትቆጥብ፣ ስትሞትም ቢሆን ታክስ ይቆረጥብሃል›› ‹‹ህዝቡ መንግሥት ይህን ሲያደርግ ለምን ዝም ይላል?›› በማለት ጠየኩ፡፡ ‹‹በሀብታሞች ይህ ነገር አይሰራባቸውም›› አለ ፈገግ እያለ፡፡ የሚገርምህ እኔ ከአንተ አባት የተሻለ ብር አገኛለሁ፡፡ ነገር ግን ከእኔ የበለጠ ታክስ የሚከፍለው እርሱ ነው፡፡ ‹‹ያ እንዴት ሊሆን ይችላል›› ስል ለእኔ ለአንድ ለዘጠኝ ዓመት ልጅ ሊገባኝ የማይችል ጥያቄ ጠየኩ፡፡ ‹‹ለምንድን ነው መንግሥት ይህን ሲሰራባቸው ዝም የሚባለው?››

ሀብታሙ አባቴ በዝምታ ተውጧል፡፡ እንደመሰለኝ ዝም ብዬ አፌ ያመጣውን ከመቀባጠር ይልቅ ዝም ብዬ እንድሰማው የፈለገ ይመስለኛል፡፡ መጨረሻ ላይ ዝም ማለትን መረጥኩ፡፡ የሰማሁትን ነገር ሁሉ አልወደድኩትም፡፡

ድሃው አባቴ በተከታታይ በሚከፍለው ከፍተኛ ታክስ እንደሚያማርር አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን አንድም የሰራው ነገር የለም፡፡ ህይወት በዙሪያዋ እየገፋቸው ነው ማለት ነው?

ሀብታሙ አባቴ ወንበሩ ላይ እንደ ተቀመጠ ትክ አድርጎ ከተመለከተኝ በኋላ ‹‹ለመማር ዝግጁ ነህ?›› ሲል በድጋሚ ጠየቀኝ፡፡ አውንታዬን አንገቴን በመነቅነቅ ገለፅሁለት፡፡

‹‹ቅድም እንደተናገርኩት ብዙ አይነት ትምህርት አለ፡፡ ለአንተ የሚያገለግል ገንዘብ እንዴት ማግኘት እንደምትችል የምትማረው የሙሉ ህይወት ትምህርት ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ኮሌጅ ውስጥ ይገቡና 4 ዓመት የሚሆን ተምረው ይጨርሳሉ፡፡ እኔ ግን እንዴት ስለ ገንዘብ የምማረው ትምህርት ህይወቴን ሙሉ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ምክንያቱም ብዙ ለማወቅ በጣርኩ ቁጥር ብዙ የማወቅ ፍለጎቴ እየጨመረ ይመጣልና፡፡ ብዙዎች ግን ይህን ትምህርት አያጤኑትም፡፡ ስራ ይሄዳሉ፤ ክፍያ ይከፍላሉ ቼክ ቡካቸውን ባላንስ ያደርጋሉ አለቀ በቃ፡፡ ሁሉም ሆኖ ደግሞ እንዴት የገንዘብ ችግር እንዳለባቸው ይገርማሉ፡፡ በመሆኑም ብዙ ብር ችግራቸውን እንደሚፈታው ያምናሉ፡፡ ጥቂቶች ግን ችግሩ የተፈጠረው ስለ ፋይናንስ ባላቸው ትምህርት ምክንያት እንደሆነ ይገነዘባሉ፡፡

ውድ አንባቢያን የፅሑፍ አቀራረብ ለየት ያለ ቢሆንም በውስጡ ያሉትን ነጥቦች ግን ነቅሳችሁ ለማውጣት እንደማይሳናችሁ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ይህ ሁኔታ በእናንተ ህይወት ቢከሰት ምን ትወስኑ ይሆን? ዲግሪና ማስተርስ መያዝ ገንዘብ ለመፍጠር መሰረት ናቸው ትላላችሁ? ያለ ክፍያ መስራቱን እንዴት አያችሁት? ለገንዘብ መስራት ሊባልና ገንዘብ ለእኛ እንዲሰራ መማር ሲባል ምን ማለት ይሆን? ህይወት እየገፋቻችሁ ነው እየገፋችኋት? ሰው ለምን ድሃ ይሆናል? አዕምሮህን በአግባሁ ተጠቅሜበታለሁ ብለህ ታስባለህ? የዛሬው ፅሑፌ እነዚህን ጥያቄዎች መልሶ ያለፈ ነው፡፡ በዚህ ግን አያበቃም ደጋግማችሁ አንብቡት፡፡ እስከ ሳምንት ሰላም ሁኑልኝ፡፡

 

Health: ጎረምሶች በልጃገረዶች የሚማረኩባቸው 24 ምክንያቶች

$
0
0

sexy lip
1. ሁልጊዜም እነሱ ማራኪ መዓዛ አላቸው፤ ክሬምና ሻምፖ ተቀብተውም ቢሆን እንኳን፤
2. ሁልጊዜም ልጃገረዶች ከትከሻችሁ አጠገብ ጭንቅላቶቻቸውን በተፈላጊው ሰዓት በትከሻዎቻችሁ ትይዩ ስታገኙት የሚፈጠርባችሁ የርህራሄ ስሜት፡፡
3. ሁልጊዜም ልታቅፏቸው ስትፈልጉ አንገታቸው ለክንዶቻችሁ ተመጣጣኝነት ስላላቸው፡፡
4. ሊስሟችሁ በዚያን ሰዓት በዓለም ላይ ድንገተኛና ትክክለኛ የሆነውን የማይረሳ ደስታ ስለሚሰጥ፡፡
5. በሚመገቡበት ጊዜ የሚያሳዩት እርጋታ፣ የሚታይባቸው ዝምታ፣ ማራኪነት፡፡
6. ሲለባብሱና ሲዘንጡ ብዙ ሰዓት መፍጀታቸው የሚያበሳጭ ቢሆንም፤ በመጨረሻ ግን በተሻለ ጥራትና ውበት ልዩ ሆነው ስለሚቀርቡ፡፡
7. ከቤት ውጪ ያለው የአየር ፀባይ መጠን ወደ ዜሮ ዲግሪ የወረደ ቢሆንም እንኳን ሁልጊዜም ሞቃታማና ፍልቅልቅ፣ የሙቀት መስህብ ስለሀነ፡፡
8. ምንም አይነት ልብስ ይልብሱ የማያምርባቸው የልብስ አይነት የለም፡፡ በሩሲያ ምሳሌያዊ ንግግር ውስጥ ‹‹የ13 ዓመት ልጃገረድ ያደረገችው የባርኔጣ ዝርያ ሁሉ ያምርባታል›› ወይም በአሁኑ ዘመን እንደምናየው የተሰራችው የፀጉር እስታይል ሁሉ… ያጠለቀችው መነፅር ሁሉ… ያንጠለጠለችው ሎቲ ሁሉ… ያደረገችው አንባር ሁሉ…
9. በዚያኛው በኩል ያለውን ህብር የመፍጠር ፍላጎት ያህል ወይም በተሻለ ሁኔታ ክፍተቱን (ጎዶሎውን) የመሙላት እኔነታቸው፡፡
10. ድርድር ሲያካሂዱ የሚያሳዩት ፅሞና እና እርካታ፡፡
11. እጆቻችንን መያዝ በፈለጉ ጊዜ እንዴት በቀላሉ ሊያገኟቸው የሚችሉበት ዘዴ፡፡
12. ፈገግታቸውና አሳሳቃቸው፡፡
13. ወንዶች በአንድ ነገር ጎበዝ ሆነው ሲሸለሙ ከማንም እንኳን ደስ አለህ ከሚል በርካታ ስሞች መሃል የእነሱን ስናገኝ የሚፈጠርብን ስሜት፡፡
14. ከተዋወቃችኋቸው አንድ ሰዓት ያልሞላ እንኳን ቢሆንም ‹‹ከዚህ በላይ የሚያቃቅር ነገር ባንነጋገር እና በምንግባባቸው ጉዳዮ ላይ ይበልጥ ብናተኩር›› የሚለው አይነት የአቀራረብ ዘዴያቸው፡፡
15. በጣም ጥሩ ነገር ስታደርጉላቸው ደስታቸውን ለመግለፅ የሚጠቀሙበት የአሳሳም ዘዴ፡፡
16. አፈቅርሻለሁ ባልና ሰዓት አይኖቿ ውስጥ የሚንተከተኩው የስሜት እሳት የሚፈጥረው ማግኔታዊ መስህብ፡፡
17. አስተቃቀፋቸው ደስ ሲላቸውም ይሁን ሲያዝኑ እንዴት አደርገው እንደሚያቅፉ፡፡
18. በተለይም ሲያለቅሱ እንዴት አድርገው ነው እቅፋቸው ውስጥ የሚወድቁት፡፡
19. ይቅርታ የሚጠይቁበት ብልሃትና መንገድ፡፡
20. ተቆጥተው እንኳን ሊመቷችሁ ሲቃጡ የሚመቱበት ቦታና ልስላሴው ርህራሄ የታከለበት መሆኑ፡፡
21. ባንቀበለውም እንኳን ላደረጉት ነገር መፀፀታቸውን የሚያሳዩበት መንገድ፡፡
22. አትተወኝ፣ አትራቀኝ እፈልግሃለሁ፣ እመኝሃለሁ፣ ላጣህ አልሻም፣ የሚሉባቸው ዘዴዎች፡፡
23. አንተ በተራህ አትተዪኝ፣ እፈልግሻለሁ፣ እመኝሻለሁ፣ ላጣሽ አልሻም በምትላቸው ጊዜ ሃሳባቸው ተቃራ ቢሆንም እንኳን የሚቀበሉበት መንገድ፡፡
24. ዓለምን አካባቢያቸውን፣ ደህንነታቸውን፣ ፍቅራቸውን ለመጠበቅ ሲሉ በሚያፈሱት እንባና በአለቃቀስ ዘይቤአቸው፡፡
ስትወዳቸው ወይም ስትጠላቸው እነርሱ የሚያስቡበት መንገድ አንተን ካጡህ ሞት ብቻ የሚታያቸው መሆኑን ወይም በተቃራኒው እነሱን ለብቻቸው ጥለሃቸው ለብቻህ ልትሞት መወሰንህ ሆኖ ነው የሚታያቸው፡፡ ምክንያቱም ከአንተ ጋር ፍቅር ከጀመሩ በኋላ ለአንተ ልባቸውን ከከፈቱ በኋላ በህይወትም በሞትም መነጣጠል የለም ብለው ስለሚያምኑ ነው… ትክ ብለህ ስታያቸው በነፍሳቸው መጠን ወይም በዘብራቃ ድምፅ ቃና ቢስ ንግግር እያደረግህም ቢሆን እንኳን ሞቱን የጠበቀ የፍቅር ህብር እየሰጠ ሸካራውን የሚያለሰልስ ልብ ነው ያላቸው፡፡
ልጃገረዶችን ወደ ሚሊዮን በሚጠጉ የተለያዩ ምክንያቶች እናፈቅራቸዋለን፡፡ በአካል ብቻ ሳይሆን በልባችንም ጥልቀት ጭምር፡፡

እሪ በይ ሃገሬ

$
0
0

ethiopian flag

ከአብርሃም ያየህ

ይህች  “እሪ በይ ኣገሬ” የተሰኘች ኣጭር ስንኝ፤ በኣሰብ ወደብ ያንድ የውጭ ባለሃብቶች የመርከብ ወኪልና የግምሩክ ኣስተላላፊ ትራንዚት ኩባንያ ቅርንጫፍ ስራ ኣስካያጅ በነበርኩበት ወቅት ታሪካቸውን በቅርበት ለማውቅላቸው፤

  • ለኣንጋፋው ኢትዮጵያዊ ስራ ፈጣሪና፥ ታላቅ ኣገር ኣልሚ ለሆኑት፤ 
  • ከትቢያ ኣፈር ተነስተው ዝነኛውን  የኢትዮጵያ ኣማልጋሜትድ ኩባንያ በመመስረት፥ ውድ ዋጋ በማስከፈል ህዝብ ሲበዘብዙ የነበሩትን የውጭ ኣገር ኩባንያዎችን በህጋዊ የዋጋ ውድድር ከገበያ ለማስወጣት ለቻሉት፤ 
  • በዚህ ኩባንያቸው ኣማካኝነትም በብዙ መከራ ያሳደጋቸውን የኢትዮጵያ ድሃ ገበሬን ህይወት ለመለወጥ ሲያኮበክቡ የ66ቱ “ኣብዮት” ደርሶ በሚያሳዝን ሆኔታ ላደናቀፋቸው፤ 
  • “ከኑግ ጋር የተገኘህ ሰሊጥ ኣብረህ ተወቀጥ” እንዲሉ፥ እኒህ ያንድ ድሃ ጭሰኛ ገበሬ ልጅ የሆኑትና፥ ምንም እንከን ሳይኖርባቸው በደርግ ማጎሪያ ቤት ለረጅም ዓመታት ለተሰቃዩት በኋላም ለስደት ለተዳረጉት፤ 
  • የማሌሊት/ወያነ ትውልደ ኤርትራዊያን መሪዎችና ግብረ-በላዎቻቸው ኣምርረው የሚጠሏትን ኢትዮጵያ እንደተቆጣጠሩ፥ የወራሪዎቹን ማንነት በውል ሳያወቁ በየዋህነት ወዳገራቸው ተመልሰው ባላቸው ከፍተኛ የስራ ልምድና እውቀት ኣማካኝነት ላገራችንና ለዝባችንን ከፍተኛ ጥቅም ለማበርከት ታጥቀው ቢነሱም፥ በደርግ እግር በተተኩት የህዝብ ጠላቶች፥ ኣገር ኣስገንጣዮችና ዳር-ድንበር ኣስደፋሪ ወያኔ/ማሌሊቶች እብሪት፥ የሚወዷትን ኣገራቸው ጥለው ለዳግም ስደት ለተዳረጉት፤ 
  • በቀ. ኃይለ-ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በኢትዮጵያ ገበሬዎችና በቅርብ በሚያውቋቸው የወቅቱ ፖለቲካ እቀንቃኞች “ተራማጅ ነጋድራስ” የሚል እውቅና ለተሰጣቸው ለክቡር እምክቡራን ላቶ ገብረየስ ቤኛ የክብር ማስታወሻ ትሁንልኝ! 

እሪ በይ ኣገሬ

እሪ በይ ኢትዮጵያ ፥ ቅል ድንጋይ ሰበረ፤

ውሃ ሽቅብ ወጣ ፥ ዘመን ተቀየረ፤

ሌባ እየከበረ ፥ ነጋዴው ከሰረ፤

ኣገር ፈራረሰች ፥ ድንበር ተደፈረ፤

እንደ ቅርጫ ስጋ ፥ እየተመተረ፤

ላረብ ለድርቡሹ ፥ ይታደል ጀመረ፤

ጀግና ኣንገቱን ደፋ ፥ ባንዳ ተወጠረ።

(ግጥም፤ ከኢየሩሳሌም ጀማል Facebook የተወሰደ።)

ኣንጀት የሚያሳርረውና የሚያበግነው፥ ኣቶ ገብረየስ ቤኛ ከኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) ጋር ያደረጉት፥ በኣምስት ክፍል የቀረበ፥ ሰፊ የምስል (የቪዲዮ) ቃለ-መጠይቅ በትዕግስት በመመልከት፥ ኣሁን በኢትዮጵያ ቤተመንግስት የሰፈሩትና ፍፁም ፀረ-ኢትዮጵያ የሆኑት ኣደገኛ የዲያብሎስ ልጆች ምንነትና ኣጥፊ ዓላማ በትክክል ለመረዳት ያስችላል። በወያነ/ማሌሊት ኣመራር ምንነት ኣሁን ያለዎትን መረጃ በማዳበር ቢሆንም ተጨማሪ ኣቅም ይገነባል።  

  

Part-1: http://ethsat.com/video/esat-yesamintu-engeda-gebreyes-begna-august-2014-part-1/

Sport: ሳላዲን ሰዒድ ኢትዮጵያ ከማሊ ጋር ባለባት ወሳኝ ጨዋታ ላይ አይሰለፍም ተባለ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና በአሁኑ ወቅት ለግብጽ አህሊ ቡድን የሚጫወተው የብሔራዊ ቡድናችን የፊት መስመር ተጫዋች ሳላዲን ሰዒድ በደረሰበት ጉዳት የተነሳ ኢትዮጵያ ከማሊ ጋር ላላት ወሳኝ የአፍሪካ ዋንጫ እንደማይሳተፍ የስፖርት ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ገለጹ።

615x340_can2013_nigeria_ethiopieአህራም የተባለው የግብጽ ጋዜጣ እንደዘገበው ኢትዮጵያዊው አጥቂ እሁድ ሴፕቴምበር 21 ቀን 2014 ዓ.ም ለክለቡ በሚጫወትበት ወቅት በደረሰበት ከባድ ጉዳት ለስድስት ሳምንታት ያህል ከሜዳ ይርቃል።

የ25 ዓመቱ ሳልሃዲን በግብጽ ስፖርት ውስጥ “የግብጽን የክለቦች ዋንጫ በማንሳት የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ” ተብሎ በታሪክ ተጽፏል።

ዋሊያዎቹ በ2015ቱ የሞሮኮ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከማሊ ጋር ለሚያደረጉት ጨዋታ ለብሔራዊ ቡድኑ የተመረጡ ተጫዋቾችች ይፋ ሲሆን የሳላዲን ተመርጦ ነበር። ምንም እንኳ በፖርቱጋላዊው አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሪቶ የሚመሩት ዋልያዎቹ ከአልጀሪያና ከማላዊ ብሔራዊ ቡድኖች ጋር ተጫውተው ድል ባይቀናቸውም በቀጣይ ከማሊ አቻቸው ለሚኖራቸው ግጥሚያም የተመረጡ ተጫዋቾች አስታውቀዋል።

በዚህም መሰረት ሲሳይ ባንጫና ታሪኩ ጌትነት ከደደቢት እግር ኳስ ክለብ እንዲሁም ጀማል ጣሰው ከኢትዮጵያ ቡና ክለብ በግብ ጠባቂነት ተመርጠዋል፡፡

አሉላ ግርማ፣ አበባው ቡጣቆ፣ አንዳርጋቸው ይላቅና ሳላዲን በርጌቾ ከቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ፣ ብርሃኑ ቦጋለና አክሊሉ አየነው ከደደቢት እግር ኳስ ክለብ ፣ ቶክ ጃምስ ከኢትዮጵያ ቡና ክለብ፣ዋሊዳ አታ ከሲውድንና አንተነህ ተስፋዬ ከአርባ ምንጭ ከነማ ተከላካዮች ናቸው፡፡

የአማካይ ስፍራ ላይ ወጣቱ ተጫዋች ናትናኤል ዘለቀ፣ አዳነ ግርማ፣ ምንተስኖት አዳነ፣ ምንያህል ተሾመ ከቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ተመርጠዋል፡፡

አስራት መገርሳ ከዳሽን፣ታደለ መንገሻ ከደደቢት፣ ዳዊት እስጢፋኖስ ከኢትዮጵያ ቡና፣ ፍሬው ሰለሞን ከመከላከያ ክለብ እንዲሁም ሽመልስ በቀለ ከግብጽ ፔትሮ ጀት ክለብ የመሃል ተጫዋች ናቸው፡፡ ሳላህዲን ሰይድና ኡመድ እኩሪ ከግብጽ፣ ጌታነህ ከበደ ከደቡብ አፍሪካ፣ አፍሬም አሻሞ ከኢትዮጵያ ቡና፣ አሚን አስካር ከኖርዌይ ዳዋ ሆትሴ ክለብ የብሔራዊ ቡድኑ የአጥቂ ክፍል ተጫዋቾች ሆነው መመረጣቸውን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።


Sport: ከ2019 እስከ 2023 የሚደረጉ የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮችን የሚያዘጋጁ ሃገራት ታወቁ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ከ2019 እስከ 2023 ድረስ የሚደረጉ የአፍሪካ ዋንጫዎችን የሚያዘጋጁ ሃገራት ዝርዝር ታወቀ። እነዚህን 3 የአፍሪካ ዋንጫዎች ማለትም የ2019 እና የ2021 የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀትም አልጄሪያ፣ ካሜሩን፣ ጊኒ፣ ኮትዲቯር፣ጋቦን፣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ እና ዛምቢያ በእጩነት ቀርበው ነበር።
FBL-WC2014-ETH-RSA
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን ወይም ትንሹ ሲጠራ “ካፍ” የ2019 እና የ2021 እና 2023 የአፍሪካ ዋንጫን እንዲያስተናግዱ የተመረጡ ሃገራትን ይፋ ሲያደርግ ጥያቄያቸው ውድቅ የሆነባቸው እጩ ሃገራት የማዘጋጀት አቅማቸውንና ፍላጎታቸውን የሚያሳይ እና የሚያስተዋውቅ የ30 ደቂቃ ቪድዮ በአፍሪካ አንድነት ድርጅት ከካፍ አባል አገራት ለተውጣጡ ተወካዮች ቀርቦ ነበር።

በዚህም መሰረት፡

– የ2019ን የአፍሪካ ዋንጫ ካሜሮን
– የ2021ን የአፍሪካ ዋንጫ አይቮሪኮሰት
– የ2023 የአፍሪካ ዋንጫም በጊኒ እንዲደረግ ወስኗል።

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ለማሰዳዳት

የ2017ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ ይሁንታን አግኝታ የነበረችው ሊቢያ ውድድሩን እንዳታስተናግድ መከልከሏን ተከትሎ፥ በርካታ ሀገራት ውድድሩን ለማዘጋጀት ፍላጎታቸውን ያሳዩ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ በበኩሏ ውድድሩን ለማዘጋጀት ያላትን ፍላጎት ጨምሮ ፤ ለውድድሩ ብቁ የሚያደርጓትን ዝርዝር ነጥቦች በካፍ ቀነ ገደብ መሰረት በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን በኩል እንደምታቀርብ ተገልጿል።

ቅኔና አዘማሪ –ከቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

$
0
0

ቀሲስ አስተርዕየ

ቀሲስ አስተርዕየ

nigatuasteraye@gmail.com
መስከረም ፳፻፯ ዓ.ም.

http://www.medhanialemeotcks.org/

መግቢያ

ለአዘማሪ ሙያ ተስማሚ የግብር መግለጫ መሆን ያለበት የቱ ነው? አዘማሪ ወይስ አርቲስት? በሚል በአቶ ዓለም ነጻነት ሬድዮ የቀረበው ውይይት ለዚህች ጦማር መነሻ ሆኖኛል።ከቀደሙ አባቶች እንደሰማሁት አዘማሪ ብቻውን የቆመ አይደለም። ከብዙ ነገሮች ጋራ ከቅኔያችን፣ ከዜማችንና ከስሜታችን ጋራ የተያያዘ ነው። አዘማሪ የሚለውን ቃል ከነዚህ ነጥሎ ለማቅረብ መሞከር ያዘማሪን ክብርና ቦታ ዝቅ ያደርገዋል የሚል ስጋት አለኝ።

ስለዚህ አዘማሪ ወደሚለው ቃል ዘው ብለን ከመግባታችን በፊት የአዘማሪን ተልእኮ መዳሰስ ሊኖርብን ነው። አዘማሪ የሚለው ቃል የግብሩ (የተልእኮው) መግለጫ ነው። ተልእኮውም ራሱ አዘማሪ ተቀኝቶም ሆነ ገጥሞ ወይም ሌላ የተቀኘውን በዝማሬው ቅላጼ ከጉሮሮውና ከመሳሪያ ጋራ አስማምቶ፣ ቀምሞና አስወድዶ አስውቦ ለህዝብ ማቅረብ ነው። ህዝቡንም ከባህሉ ከታሪኩ ከኢትዮጵያዊነቱ ከስሜቱ ጋራ እርስ በርሱ የበለጠ ያጣብቃል። እርስ በርሱ ያቀራርባል። ያዋህዳል። ያስተባብራል። እንደ ኢትዮጵያ ከመሰለ በቅኝ ግዛት ሳይወረር የራሱን ጠብቆ ከሚኖር አገር የሚፈልቅ አዘማሪ የሚያስተላልፈው ቅኔ፦ ኅብር፤ ሰምና ወርቅ፤ ሰረዝ፤ ጎዳና፤ ውስጠ ወይራና ሌላም ዓይነቶች አሉ። ያዘማሪን ክብርና ቦታ ዝቅ ላለማድረግ ስለአዘማሪ ከመናገሬ በፊት ስለኢትዮጵያዊ ቅኔ ትንሽ ማብራሪያ መስጠት ፈለኩ።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

በኦጋዴን ክልል የሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ የተደረገውን የጅምላ ጭፍጨፋ እናወግዛለን

$
0
0

entc-logo-5አገር በቀል የሆነው፤ የቅኝ አገዛዝና ዘረኛው የወያኔ ሰርአት በኦጋዴን ክልል የሚኖሩ ወገኖቻችንን ከተቃዋሚ ድርጅት ጋር ግንኙነት  አላቸው በሚል ሽፋን ያደረገውን የጅምላ ጭፍጨፋና ጭፍጨፋውን ተከትሎ አስከሬን መሬት ለመሬት እየተጎተተ እንዲከማች  መደረጉን በመስከረም 5 ቀን 2007 ዓም በኢትዮጵያ ሳተላይት ቴለቪዥን በመረጃነት የቀረበውን ዘግናኝ ድርጊት ተመልክተናል። የዚህ  ዘግኛኝ ወንጀል አስፈጻሚ የሆኑ ግለሰቦችም የወገኖቻችን አስከሬን እነደእንስሳ እያስጎተቱ ባንድ ቦታ እንዲከማች ትዛዝ  በሚያስተላልፉበት ወቅት ሲናገሩት የነበረውን ማድመጥ ልብ የሚሰብረና አይምሮን የሚሰቀጥጥ ነው። የኢትዮጵያዊ ብሔራዊ የሽግግር  ምክር ቤት ይህን ፋሽስታዊ ድርጊት በጽኑ ያወግዛል።—  ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—-

የመጀመሪያዋ በጐ ፈቃደኛ የኢቦላን የሙከራ ክትባት ወሰደች

$
0
0

አሜሪካ 300 ወታደሮች ወደ ላይቤሪያ ልትልክ ነው

እንግሊዛዊቷ የኮሙኒኬሽን ባለሙያ ሩት አትኪንስ ሰሞኑን በኦክስፎርድ ለ60 በጎ ፍቃደኞች ሊሰጥ የታቀደውን
የኢቦላ ቫይረስ የሙከራ ክትባት በመውሰድ የመጀመሪያዋ በጎ ፈቃደኛ እንደሆነች መሆኗን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
የሙከራ ክትባቱን የሚወስዱ በጎ ፈቃደኞች እንደሚፈለጉ በቢቢሲ ሬዲዮ መስማቷን የገለፀችው አትኪንስ፣
በምዕራብ አፍሪካ ሁኔታው በጣም አሳዛኝ ስለሆነና የዚህ ክትባት ሂደት አካል መሆን ትልቅ ውጤት ለማምጣት
በሚደረገው ጥረት ማበርከት የምችለው ትንሹ ነገር እንደሆነ በማሰብ፣ ክትባቱን በበጎፈቃደኝነት ለመውሰድ
ወስኛለሁ” ብላለች፡፡
ክትባቱ ከኢቦላ ቫይረስ ትንሽ የዘረመል ንጥረ ነገር ብቻ የያዘ በመሆኑ ተከታቢው በበሽታው እንደማይያዝ
የተገለፀ ሲሆን በኦክስፎርድ የጄነር ኢኒስቲቲዩት ዳይሬክተርና የሙከራ ክትባቱ መሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አድርያን
ሂልም፤ “ይሄ ክትባት ማንንም ኢቦላ ያስይዛል የሚል ቅንጣት ስጋት የለም” ብለዋል፡፡
ክትባቱን ለመወጋት ስታስብ የደህንነቷ ጉዳይ እንዳላስጨነቃት የተናገረችው ሚስ አትኪንስ፤ የ15 ዓመት ታዳጊ
ልጇ የኢቦላ ቫይረስ ተሰጥቷት የምትሞት መስሎት እንደነበርና እንዳረጋጋችውም ገልፃለች፡፡
ብዙ ጊዜ አዲስ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል ፈቃድ ከማግኘቱ በፊት ለዓመታት በሰዎች ላይ ሙከራ ሲደረግ
ይቆይ ነበር ያለው ቢቢሲ፤ በምዕራብ አፍሪካ የተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ አጣዳፊነት ግን ይሄ የሙከራ ክትባት
በአስደናቂ ፍጥነት ጥቅም ላይ እንዲውል ጥረቱ እንዲጠናከር አድርጓል ብሏል፡፡
በሰዎች ላይ የሚደረገው ሙከራ ውጤታማ ሆኖ ከተገኘ፣ ክትባቱ በፈረንጆች ዓመት መጨረሻ ላይ በቫይረሱ
በተጠቁ አካባቢዎች የሚገኙ የጤና ሰራተኞችን ከበሽታው ለመከላከል ጥቅም ላይ እንደሚውል ታውቋል፡፡
ያን ጊዜ ግን ለ10ሺ ሰዎች ያህል የሚሆን ክትባት እንደሚያስፈልግ የተገለፀ ሲሆን በምዕራብ አፍሪካ ክፉኛ
የተጠቁ አካባቢዎች ላይ የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎችን ከቫይረሱ ለመከላከል ጥቅም ላይ ይውላል ተብሏል፡፡
ክትባቱ እየተሰራ የሚገኘው ግላክሶስሚዝክላይን በተባለ ኩባንያና በአሜሪካ ብሔራዊ የጤና ተቋም ሲሆን፣
የእንግሊዝ ዓለምአቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅትን ጨምሮ የተለያዩ የምርምር ተቋማት ለሙከራ ክትባቱ የገንዘብ
ድጋፍ እንዳደረጉ ታውቋል፡፡
በሌላ በኩል የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ የኢቦላ ቫይረስን ለመከላከል እገዛ የሚያደርጉ 3ሺ ወታደሮችን
ወደ ላይቤሪያ የመላክ ዕቅድ እንዳላቸው ባለፈው ማክሰኞ አስታወቁ፡፡ ኦባማ ይሄን ያስታወቁት የላይቤሪያዋ
ፕሬዚዳንት አለን ጆንሰን ሰርሊፍ በሽታውን ለመከላከል እገዛ ያደርጉላቸው ዘንድ ለኦባማ በቀጥታ ያቀረቡትን
ጥያቄ ተከትሎ እንደሆነ ታውቋል፡፡
የአሜሪካ ወታደራዊ ሃይል የህክምና ማዕከሎችን ግንባታ በመቆጣጠርና የጤና ሰራተኞችን በማሰልጠን
ለላይቤሪያ መንግስት እገዛ እንደሚያደርግ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በምዕራብ አፍሪካ ለተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ የዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ፈጣን ያልሆነ ምላሽ ትችት ሲሰነዘርበት
፣ቆየቱ ይታወቃል፡፡
በበሽታው ክፉኛ የተጠቁት የምዕራብ አፍሪካ አገራት ሴራሊዮን፣ ላይቤሪያና ጊኒ ሲሆኑ ወረርሽኙ ከ2400 በላይ
ሰዎችን ለህልፈት እንደዳረገ ተጠቁሟል፡፡ ከእዚህ የሞት አደጋ ውስጥ ግማሹ የተከሰተው በላይቤሪያ ነው፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት፤ አገሪቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ተጨማሪ ሰዎችን በቫይረሱ ልታጣ እንደምትችል በቅርቡ
አስጠንቅቋል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኃላፊዎች፣ በጄኔቫ በሚያካሂዱት ስብሰባ ለወረርሽኙ
በተሰጠው ዓለም አቀፍ ምላሽ ላይ እንደሚወያዩ ቢቢሲ ጠቁሟል፡፡
የጋና ፕሬዚዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ ባለፈው ሰኞ ወረርሽኙን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤
“በምዕራብ አፍሪካ ለተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ከፍተኛና ፈጣን የውጭ እርዳታ ያስፈልጋል” ብለዋል፡፡

ምንጭ፥   አዲስ አድማስ

-

“ጋኖች አለቁና ምንቸቶች ጋን ሆኑ” (ወንድሙ መኰነን)

$
0
0

ወንድሙ መኰነን

የለንደኖቹ ልማታዊ “ ካኅናት ” ወያኔያዊ ዘጋቢ ፊልምአቀናበሩብን !

ኢንግላንድ መስከረም ፯ ቀን ፪፲፻፯ ዓ.ም

መግቢያ

እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሳችሁ። መባል ስላለበት ነው። ያለፈውማ ዓመትአንደኛውን ጥቁር ዓመት ተብሏል። ሲያንሰው ነው። ወያኔ ከመቼው በበለጠ ጥቃቷን በኢትዮጵያ ልጆች ላይ በሁሉም አቅጣጫ ያጧጧፈችበት ዓመት ነበር። ነጻውን መገናኛ ብዙሀን ከጨዋታ ውጪ አድርጋለች። ብዙ ጋዜጠኞች በማሠሯ ወህኔ ቤቱ ጠቧል መሰለኝ፣ አሁን አሁን የያዘችው ዜዴ፣ በቁጥጥሯ ሥር ከሌሉ፣የፋሺን ጋዜጠኞችም ሳይቀሩ ማዘዣ ሳይደርሳቸው፣ በሬዲዮዋና በጋዜጦቿ “ከስሼአቸዋለሁ!” በማለት ፣ ነጭ ሽብር እየነዛችባቸው በርግገው ከአገር እንዲጠፉ ማሳደዷን በሰፊው ተያይዛቸዋለች።

በዓመቱ መጨረሻ ወር ብቻ 21 ጋዜጠኞች ተደናብረው አገር ጥለው እግሬ አውጪኝ ብለዋል።ሲሸሹም እያየች አታስቆማቸውም። ብቻ ሲወጡላት፣ “እስየው ተሰደዱልኝ!” ብላ “ደቁሴ ንሬ፣ ተባራብሬ!”ዋን ትደልቃልች! ወንድማችን እስክንድር ነጋ፣ እህታችን ርዕዮት ዓለሙና ሌሎች ጋዜጠኞች ብዕር ስላነሱባት ተሸብራ “ሽብርተኞች” ብላ ወህኒ አጉራቸዋለች። አንዷለም አራጌ፣ በአንደበቱ፣ “ወያኔ የሰው ልጅ መብት ረጋጭ ነው” ብሎ ጮክ ብሎ በመናገሩ ተሸብራ፣ 14 ዓመት ፈርዳበት ቃሊቲ ወርዶ ፍዳውን እያየ ነው። ነፍጥ አንስቶ አንድ ሁለቱን ቢደፋማ ኑሮ፣ “እንደራደር” እያለች አፏን ታሞጠሙጥ ነበር። አሁን በቅርብ ቀን ወያኔ እያዳፋች የወሰደቻቸው እነ ኃብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ዳኒኤል ሺበሺ፣ አብርሀ ደስታ በቃላት ካለሆነ በጥየት የት ቦታ ነክተዋት! ዕውነትም ዓመቱ የጨለማ ዓመት ነበር። የወንጀሎች ሁሉ ወንጀል ግን፣ ወንድማችንን፣ አንዳርጋቸው ጽጌን፣ አለማቀፍ የአየር ትራንስፖርት የመንገደኞችን ደኅንነት በጣሰ ሁኔታ መጥለፏ ነው። ይኸ ወንጀል ብዙዎቻችንን ቆሽታችንን አድብኖታል። ለንደን ደብርጽዮን ቅድስት ማርያምን ከሕዝቡ ቀምተው ለወያኔ ሊያስረክቡ ለሁለት ዓመታት ጎልተው የሚሞግቱን ልማታዊ ካኅናቶቿ ግን በደስታ እያሸበሸቡ ነው። እንዲያም ዘጋቢ ፊልም ሠሩብን!

ካኅን ማነው ?

አንድ ጭብጥ እንያዝ። በመጀመሪያ “ካኅን ሊባል የሚቻለው ማነው?” ለሚለው ጥያቄ መልስ ይሰጥ። ክኅነት የተቀበለ ሁሉ ካህን አይደለም። ክኅነት ደረጃ ደረጃ አለው። ከንፍቀ ሲያቆን ይጀምራል። ከዚያም ዲይቆን ይባላል። ቀጥሎም ለሊቀ ዲአቆንነት የደረሳል። ሊቀ ዲያቆኑ ን|ጽሕናውን እንደጠበቀ፣ ሲዳር (ትድር ሲይዝ) ይቀስሳል። ከዚያ በኋል ካህን ይባላል። በመሀሉ ዘማሪዎችና መሪጌታዎች አሉ። እንደሱ ካልሆነማ እኔም ካህን ልባል ነዋ! የንፍቀ ድቁና ክኅነት እኮ ተቀብዬአለሁ። ያውም ከአቡነ ቄርሎስ እጅ! አንድ የቤተ እግዚአብሔር አጋልጋይ ለካኅንነት ማዕረግ የሚበቃው፣ ቄስ ሲሆን ብቻ ነው። ዲያቆን ካህን አይደለም! ገና ይቀረዋል። የመነኰሰ ሁሉም ካኅን አይደለም። መነኵሴ በሁለት ይከፈላል። አንዱ ገና ከሕጻንነቱ/ልጅነቱ ጀምሮ እራሱን ለእግዚአብሔር የለየ ድንግል ( ይሰሙኛል አባ ተባዩ – መንደር ሲያውደ ለድል ሕይወት አጣጥሞ ከብሒራዊ ውትድርና ለማምለጥ ገዳም የተሸሸገ ወሮ – በላ ሳይሆን ከሕጻንነቱ የተለየ ድንግል !!)ባሕታዊ ነው። ይኸ ሰው ከመጀመሪያውም ለአገልግሎት የተጠራ በመሆኑ ገዳማዊ መነኵሴ ይባላል። በድቁና እያገለገለ ይኖርና፣ እድሜው ለአቅመ አዳም ሲደርስ፣ ንጽሕናው፣ ተመስክሮለት በቅስና ያገለግላል። ያ ገዳማዊ መንኵሴ ነው። ሌላው ደግሞ የዚህች ዓለም አሸሻ ገዳሜን ሲጨርስ፣ የተወሰነ የአካሉ ክፍል አልሠራ ሲለው በቃኝ ብሎ የሚመነኵስ ነው። የሶስት ዓመቱን አመክሮ ከጨረሰ በኋላ፣ ቆብ ደፍቶ ዓለም በቃኝ ያለ ነው። ያ ሰው፣ በምንም ዓይነት ሊቀስሥ አይችልም። የቀረችውን ጊዜውን አምላክን እየለምኑ ይኖርና ዓለሟን መገላገል ነው። “አባ ግርማ” ካኅን ናቸው? ካህን ጥራ ቢባል እራሱ ግሩም መጣ ተብሏል። ጋኖች አለቁና ምንቸቶች ጋን ሆኑ! ካኅን ጠብቅ የተባለውን መንጋ አይበትንም! ካህን ሥልጣን አይፈልግም። ካህን ገንዘብ አይወደም!

የለንደኖቹ ልማታዊ “ ካኅናት ” ዘጋቢ ፊልም።

አንዳርጋቸው መጠለፉን ተከትሎ፣ ወያኔ፣ ዶኩመንተሪ አይሉት ዜና፣ እንደልማዷ አንድ ዝግጅት አዘጋጅታ፣ በቴሌቪዥን ለዓለም ሕዝብ አሰራጭታዋለች። የቤተክርስቲያናችንም ጉዶች ከወያኔ ጋር በመተባበርና የወያኔን ቴሊቪዢን እንደዋና መረጃ ምንጫቸው አድርገው፣ ዘጋቢ (ዶክዩመንታሪ) ፊልም፣ ይታይላቸው እንጂ! እነሆ እየኮመኮማችሁ ተዝናኑበት!

 

 

በውስጡ የታጨቀው የወያኔ ቱልቱላ ነው። ባጭሩ ፍሬ ከርሲኪ ነው። እሱን ለተመልካቹ ተተን፣ አቅናባሪውና ተዋንያኖቹ እነመማን እንደሆነ በአጭሩ ቀርብ ብለን፣ በመረጃ ተንተርሰን እያንዳንዳቸውን እንመርምር። “ጉድና ጅራት ከበሰተኋላ ነው” የሚሉት አበው ሲተርቱ?

የስም ላጲሱ የወያኔ ፊልም ቀራጭ

እንዳለ ወንዳፍራሽ ይባላል። ሲበዛ ባሌጌ ነው። አዋራጅ ነው። የወያኔ አገልጋይ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ፣ ጥቁር መነጽርና ኩፊያ ከራሱ ወርደው አያውቁም። በፈረንጆቹ አቆጣጠር እስከሁለት ሺ ዓ.ም. ድረስ እኔን፣ የዚህ ጽሑፍ አቅራቢን በጣም ይቀርበኝ ነበር። እኔም ሰው መስሎኝ፣ አቀርበው ነበር። ጽሑፎቼንና ግጥሞቼን በአማርኛ እየተየበ፣ በራሱ አነሳሽነት እያባዛ ይበትን ነበር። በፈረንጆቹ አቆጣጠር፣ ያንን ሰው ከአገር ወዳድነት በአሻገር ለወያኔ ያገለግላል ብዬ አንድም ቀን ጠርጥሬው አላውቅም። በሬ ከአራጁ ጋር ይውላል ማለት እኔ ነኝ። የትም እንሂድ ቢለኝ፣ እሄድለት ነበር። እንገናኝ ብለኝ ምንም ሳላወላውል አገኘው ነበር። አንድ ቀን አንድ የወያኔ አራጊ ፈጣሪ ግለ ሰብ ከሚያስተዳድረው ድርጀት ሲወጣ ፊት ለፊት ተገጣጠምን። ምን እዚህ ትሠራለህ? ወያኔ መሆኑን አታውቅም አልኩት። ለጉዳይ እንደሄደ ብቻ ነግሮኝ ተለያየን። እዚያ መሥራት እንደጀመረ በተዘዋዋሪ መንገድ ደረስኩበት። ከዚያ በኋላ እሱም ሸሸኝ፣ አኔም አልፈለግኩትም። የድርጅቱ አስተዳዳሪ፣ወያኔው ባለሟል፣ “አዎንታ” የተባለ፣ ኢትዮጵያውያንን ለመጥለፍ የተዘጋጀ ድርጅት ሊቀ መንበር ነው። የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ብሎ ሐምር-ስሚዝ መሥርቶ እንደ እንዳለ ያሉትን ጠላፊዎች ቀጥሮ፣ አዲስ ስደተኞች ኢትዮጵያውያንን እየመለመሉ፣ በአምስት እያደራጁ፣ ማወየን ነበር ተግባራቸው። እነ እንዳለም፣ ኮባኒያ ፈጥረው ኮንሱልተንት ተብለው ይሠሩለት ነበር። የገንዘብ መሰብሰቢያ ኮባኒያውን ስም ለማየት በአደባባይ ከሚገኘው የመረጃ ምንጭ፣ ከ http://companycheck.co.uk/director/906368336 ማግኘት ይቻላል። በበለጠ ወደ ውስጥ ገብቶ ለማየት፣ መመዝግብ ያስፈልጋል እንጂ፣ ጉዱንና ጉድጓዱን፣ በሚቀጥለው ተቋሚhttps://www.duedil.com/company/03183927/refugee-advice-and-support-centre ወይም በዚህኛው ጠቋሚ https://www.duedil.com/director/906368336/endale-wondafrash ማየት ይቻላ። እንዳለን፣ ወያኔ ሌላ ሥራ ላይ አሠማራችው። ስደተኛውን መልሶ የወያኔ እጅ የማስገባት የኮንሰልታንሲውን ሥር ቶት ፊልም አቀናባሪአቸው ሆነ። Endexeye [i] በሚል የተበላሸ ስም፣ ብዙ ስም አጥፊ ፊልም አቀናብሮ በዩ-ትዩብ በትኗል። ሞገደኛው መነኵሴ ነኝ ባይ፣ ቤቴክርስቲያናችንን ለወያኔ ሊያስረክቡ ሲነሱ፣ እንዳለ ፊልም አንሺአቸው ብቻ ሳይሆን የወያኔ ተቃዋሚ የሆነውን ሁሉ እየተከታተለ፣ ስማችንን ማጥፋት፣ ማሸማቀቅና ማዋረድን ዋናው ተግብሩ አድርጓል። የኔንማ ተውት። ባንኪንግሀም ይኒቨርሲቲ ድረስ፣ ግብረሰዶማውያንን አስተባብሮ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያስወጣብኝ [ii] [iii] የሞከረው ጉድ፣ ነው።

አንዳርጋቸው ከተያዘ ጀምሮ እንዳለ የማይለው የለም። ቫይበር በተባለው የመገናኛ ዘዴ በሚበትነው የዕውነተኛ ሽብር ጽሑፉ፣ ከዚህ በፊት በሳውዲ አረቢያ የተጨፈጨፉትን ወንድሞችና እህቶች ምክንያት ተናደን ሆ ብለን አንድ ላይ ስንወጣ፣ እንደዓይጥ ጓዳው ውስጥ ተውሽቆ “እሰየው! እንኳን ጨፈጨፏቸው! የሳውዲ አረቢያ መንግሥት ያንን ለማድረግ መብት አለው” ባለን አንደበቱ፣ አሁንም የአንዳርጋቸው ጽጌን መወሰድ ነገር በየቀኑ ይጽፋል። እያንዳንዳችን እንደምንወሰድ እየዛተብን ይገኛል።

አሰፋ ምንተስኖት [iv] የተባሉ ጸሕፊ፣ ስለዚህ ጉዳይ በመረጃ በተደገፈ ጽሑፍ፣ ሰለዝህ ጉደኛ ሰው፣ ጽፈዋል። ታዲያ እንዳለ፣ Atse Tewodrose II በሚል የውሸት ስም 12 ጊዜ ተንገብግቦ አስተያየት ኢካዲኤፍ ድረ ገጽ ላይ ዘባርቋል። የሚገርመው ነገር፣ ስለእያንዳንዳችን እንደፈለገ ተንስቶ ሲመርግብን፣ አንድ አሰፋ ምንተስኖት በጻፉት ጽሑፍ፣ ያን ሁሉ እየተንገበገበ መጻፉ ነው። ለዚህ ሰውዬ አንድ መርዶ አለኝ። ወንድሙ መኰንን፣ እንኳን ለእንደዚአህ ያል ፍርፋሪ ለቃሚ የወያኔ ቡችሎች፣ ለአሳዳሪ ጌቶቻችሁም ስሜን ደብቄ እንደማላቅ ነው! ግሩምን መሰልኩ እንዴ አባቴና እናቴ ያወጡልኝ ስም ወደ ግሩማ የምቀይረው? “አይ አለማወቅሽ አገርሽ መራቁ!” አለ ሰውዬው! ጌቶቹንም ብግን የሚያደርጋቸው ይኸው ነው። እነሱ ስማቸውን ይደብቁ እንጂ እኔ ምን ነውር ሠርቼ፣ እኔ ምን ተዳዬ!

አንዲት እህት ስለዚህ ጉደኛ ፍጡር ብግን ብላ ስትናገር “ትንሽ እንጀራ ወጥ ይጨርሳል፣ ትንሽ ሰው ሰው ያሳንሳል” ብላዋለች። እንግዲህ ወያኔ ከመደበችብን በቤተክርስቲያናችን ውስት የፕሮፓጋንዳው ክፍል አራጌ ፈጣሪ ይኸው ሒሊና ቢዝ ሰው ነው።

“ ካኅን ” እንበለው “ አርበኛ ”

ግራ የገባው ነገር እኮ ነው። ሰውዬው አርበኛም አልነበረም ካህንም አይደልም። ጋኖች አለቁና ምንቸቶች ጋን ሆኑ! መንገሻ መልኬ አርበኛ ነው “ካህን”? በየትኛው ሒሳብ? እንኳን ካህን ሊባልና ለድቁና መብቃቱንም ማረጋገጫ እስካሁን አልተገኘለትም። ስለዚህ ሰው ብዙ ብዙ አሳፋሪ ምግብሮችን እንሰማለን። ወያኔ የሚጠቀምበትን ዕቃ ካገኘ፣ ሥነ-ምግባር ጉዳዩ አይደልም። አንድ ነገር ብቻ ለምሳሌ ልጥቀስላችሁ። ሰውዬው እንደመጣ ሲነግረን የነበረው ጸረ-ወያኔነቱን ነው። ከአንዲት ሰላማዊ ሰልፍ ቀርቶ አያውቅም ነበር። እኔማ ሞኙ፣ የዋህ የተገፋ የአገሬ ልጅ መስሎኝ፣ እንደወንድሜ ስፍስፍ ነበር የምልለት። ወያኔን ማስወገድ የሚቻለው በነፍጥ ብቻ መሆኑን አጥብቆ ተከራካሪ ነበር። አሁን አሁን እንዲዚህ ዙሮ የወያኔ መንከሻ ጥርስ ሊሆንብን! ጠረጠርኩት! ስለአርበኝነት ካነሳን አይቀር፣ መንገሻ መልኬ የአርበኞች ግንባር አባል ነበር። የአርበኞች ስብሰባ ላይ፣ ቀስቃሽ፣ አራጌ ፈጣሪ፣ እልፍኝ፣ አስከልካይ ነበር። ማመን ያዳግታል አይደል? ካሜራና ሞኝ የያዘው አይለቅ! ይኸውና!

ይኸ ነው ካህን? ድንቄም የቅድስት ማርያም “ካኅን!” ትንሽ ዕውቀት አደገኛ እንዲሉ! እንዳለ ወንዳፍራሽ መንገሻን የወያኔ ክኅነት ካባ አጥልቆለት “መጥ” አስብሎታል። ጉድ እኮ ነው! ተሰጥዖ እንኳን መመለስ የማይችል፣ ካህን ተባለ? ይኽቺ ናት የወያኔ ካኅን! “ጉድና ጅራት ከወደኋላ” ነው የሚባለው! ለይምሰል አመንኵሰው በየገዳማቱ የሰገሰጉት ነፍሰ ገዳይ ሁሉ ዛሬ ለቆሞስነትና ጵጵስና በቅቶ የለ? መንገሻ ከመጽሐፍ ቅዱስ ዕውቀት በስተቀር ከነዚአይ በምን ያንሰዋል! ቁመቱን እንዲሁ ሰጥቶታል። “ረዥም ባይፈራ አጭር ባይኮራ ነው” የሚባለው? እንዲያው በሞቴ፣ ከላይ ያያችሁትን ፊልምና ከዚህያቀርብኩላችሁን ፎቶግራም ስታዩ አንድ ነገር አልከነከናችሁም? አንዳንድ ሰዎች በየቀኑ እስሥት ይመስል አቋማቸውን ለምን ይሆን የሚለዋውጡት? ሕሊና-በስ በመሆናቸው!

“ መሪ ጌታ ” ካኅን ነው ?

የአንተ ያለህ! “የት ይደርሳል የተባለ ጥጃ ልኳንዳ ቤት ተገኘ!” ይሉሀል ይኸ ነው። መንገሻስ ስለሀይማኖት የሚያውቀው ነገር ስለሌለ፣ እሺ ይንከሰን፣ መሪ ጌታ ተባዩ ኼኖክ፣ “ሊቀ-ሊቃውንቱ” ምነዋ የመጽሐፍ ቅዱስን ሀ-ሁ ጠፋው??? ወያኔ አዞረበት እንዴ! እኮን ጉድ ነው! መሪ ጌታ ኸኖክና የወያኔ መንከሻ ጥርስ እየተቀባበሉ “መዲኃኔዓለምበአደራ ያስረከበኝንመንጋ በትኜ አልተባበራችሁም” ብለውከኛ ጋር በርብዱ፣ በውርጩ፣ በጽሐዩ፣በዝናቡ የሚንከራተቱትን ካኅን፣ መልአከ ብርሀን ቀሲስ ብርሀኑን ብሥራትን ሥጋቸውንእንደጅብ እየተፈራረቁ ቦጨቁ።መሪ ጌታ ሄኖክ አንድ ቀን በግዕዝ አንድ መዝሙር ተቀኝቶ መጥቶ ሲያሸብሽብ ሳየው፣ የሽብሸባውን ትርጉም እየተነተነ ሲያስረዳ፣ ሞቅ ብሎኝ ሄጄ አመሰግንኩት። የራሴን ቋንቋ በደንብሳልውቅ ባዕድ ቋንቋ (ያውም ሁለት) ስማር ያጠፋኹት ጊዜ ሳስበው ቆጨኝ። ስምንት የግዕዝ መማሪያ መጽሕፍት አስምጥቼ እራሴን ማስተማር የጀመርኩት በመንፈሳዊ ቅናት ተነሳስቼ ነበር። ትልቁ ዳቦ ሊጠ ሆነላችሁ! ለካንስ ሰውዬው ቃላቱን ከመሸምደድ ውጪ የክርስቶስ ትምሕርት በውስጡ አልተዘራም። ጋን መስሎኝ ነበር፣ ለካስ እሱም ምንቸት ኑራል?

እንግዲህ እኔ፣ መሪ ጌታ ኼኖክን መጽሐፍ ቅዱስን ላስተምረው!“ካህን እረኛ አይደለም፣ እረኛው እየሱስ ክርስቶስ ነው” ላለው መልሴ አጭር ነው። ጌታ “እኔ መልካም እረኛ ነኝ” ያለው ለደቀመዛሙርቱ፣ ነበር። ይኽቺን ዓለም ቶቶ ወደ መንበሩ ሲመለስ ግን እረኝነቱን ለካኅናቱ (ለቀሳውስቱ፣ ለኢጲስቆጶሳቱ እና ለጳጳሳቱ) አስረክቦአቸው ነው የአረገው! እናንተ ነዳፊ የእፉኝት ልጆች፣ መጽሐፍ ቅዱስ ካላችሁ አውጡ። እኔ ትንሹ፣ ልሟገታችሁ፣ እናንተ “የተለሰናችሁ ግድግዶች”ጌታ እየሱስ ክርስቶስ ደቀ-መዝሙሩን ጴጥሮስን በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፩ ከቁጥር ፲፭ እስከ ፲፯ “ግልገሎቼን አሰማራ … ጠቦቶቼን ጠብቅ … በጎቼን አሰማራ” ሲል ካኅናት ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የእረኝነትን ኃላፊነት እንደተቀብሉና እኛ ግልገሎቹ፣ ጠቦቶቹ እና በጎቹ እንደሆን ቁልጭ አድርጎ አስተምሯል። አይ መሪ ጌታ! ሳትበስል ኑሯል “መሪ” የተባልከው?

የአዋቂ አጥፊው ካህን

ሦስተኛው የወያኔ ዘገባ (ዶኩዩሜንታሪ) ቅንብር ተዋናይ፣ ከሁልቱም በትምሕርትና በመጽሐፍ ቅዱስ ዕውቀት የላቀ ነው። ቄስ አባተ ይባላል። ልብ በሉ፣ ቄስ ስል በትምሕርተ ትቅስ አላስቀመጥኩም። ለነገሩ ቄስ መሆኑን ያውቅኩት፣ ነገሮችን የወያኔ ጀሌዎች ቡክት ካደረጉት በኋላ ነው። ቢሆንም ዕውቀቱን በተመለከተ ቅስና ይገባዋል። ያገባም፣ የወለደም ነው። እንዴሌሎቹ ሲልከሰከስም አይታይም። ግን የአዋቂ አጥፊ ነው። ምን-ናካው! እነዚያ ሁልቱ፣ ስለእረኛ ሲናገሩ አዘበራርቀው ሲያወሩ፣ እሱ በትክክል ተናግሯል። ዳሩ ግን “እረኛ” የሚለው አባባል ለመላከ ብርሀን ቀሲስ ብርሀኑ ብሥራት ሽንጡን ገትሮ ተከራከረ። ታዲያ ለማን ነው የሚገባው? የቤተክርስቲያኗን በር ምዕምኑ ላይ ጥርቅም ላደረጉት ለመንጋውን በታኝ የቀበሮ ባኅታዊ ግሩምና ለራሱ አስቧት ይሆን? ሲያምረው ይቅርበት። እረኛው የክርስቶስ መንጋ ጠባቂ ነው። “የናንተ ጥቅም ባፍንጫዬ ይውጣ ብለው” የሰበሰቡን አባት ዕውነተኛ የጌታ በጎች ጠባቂ ካልተባሉ፣ በታኞቹማ የበግ ልምድ የለበሱ ተኵላዎች ናችው! አይ አባተ! “አባተ ግድግዳው ምን ሁኖ ሰከረ?” የሚል ቀልድ በልመንህ አይታችኋል? እሱም ምንቸት ሆነ። ጋኖቹ የት ገቡ?

ውይ ረስቼው! ዲያቆን አባተ፣ ቅስናውን ከማን ንበር የተቀበልው? ቀጥሎ ያለውን ደብዳቤ ምስጢሩን ይናገራል።

አባተ ለካንስ ቅስናውን ያገኘው ከአባታችን ከአቡነ ኤሊያስ ኑሯል! አባታችን የወያኔ ሲኖዶስ ሊቀ ጳጳስ ሳይሆኑ የሕጋዊው ስድተኛ ሲኖዶስ ሊቀ ጳጳስ ናቸው እኮ። ወይ ጉድ! ግሩማና አባተ ሕጋዊው ሲኖዶስ አዲስ አበባ ያለው ነው እያሉ ወዶ ገባነታቸው በመጮኽ ሲያረጋግጡ፣ዲያቆን አባተ፣ ቅሰናውን ከየት እንዳገኘው ረስተው ነውን?

ሞገደኛውና ከሀዲው መነኵሴስ ካህን ናቸው ?

እሳቸውም ያው ምንቸት ናቸው! ፖሊቲከኞች አሉን። ቅንጅት አሉን። ደርግ አሉን። ግንቦት ሰባቶች አሉን። እንሱስ ፱ ቦታ የሚረግጡ፣ ምን ሊባሉ? ካኅናት! ድንቄም!። ስደተኛውን ለሶልዲ የሸጡትን የቀበሮ ባሕታዊውን ካህናት ከተብሉ ነገሩ፣ ጋኖች አለቁና ምንቸቶች ጋን ሆኑ ነው የሚባለው። ሞገደኛው ያደረሱብንን እንግልት፣ ትሪካችንን የተከታተለ ሁሉ ያውቃል። ወሎጆቻቸው የፊት ጉዳቸውን ትተው በትክክል “ግሩም” ብለውአቸው ነበር። ሰውዬው ምኑ ዋዛ! እናት አባታቸው የወጡላቸውን ስም ተግባራቸው ስለሚያጋልጥባቸው አሽቀንጥረው ጣሉት። ትንሽ ዘውር አድርገው “አባ ግርማ” ነኝ አሉን። አልፈው ተርፈውም “ወያኔ ፈለጠኝ፣ ቆረጠኝ፤ አሳደደኝ፣ አሳበደኝ” ብለው በስደተኛነት ተመዝገበው ተቀላቀሉን። ይግርማሉ እንጂ፣ ግርማውንስ አልተላበሱትም። ሰላማዊ ሰልፍ ከኛ ጋር ወጥተው “ወያኔ ይውደም!” ሲሉ ዕውነት የተበደሉ እንጂ የቀበሮ ባኅታዊነታቸው አልታየንም ነበር። ቀስ በቀስ ስደተኛው ክርስቲያን በጃቸው ካስገቡ በኋላ፣ የቤተክርስቲያኗን ቁልፍ ተረከቡ። እወንተኛው ቀንደኛው ስይጣንነታቸዋ መጣባቸዋ! “እድሜ ልክ ካልሾማችሁኝ ብለው ቤተክርስቲያናችንን በቀብድ ያዟት! እምቢ ስንላቸው ለወያኔ አሳልፈው ሸጡን። መዋሸቱን፣ መሸፍጡን፣ ማደናገሩን እና ማወናበዱን የመርካቶም ነፍሰ በላ አይስተካከላቸውም። አራዳ!

የኛው ራስፑቲንና አሽቃባጮቻቸው

ወያኔ ድሮውንም ሌባ ትወዳለች! ከጠባቂ ዘበኛ ጀምሮ እስከ ክብር አስጠባቂዎች ቀጥራ አቁማላቸዋለች። እንደ ራስፑንም አሽቃባጭ ወጣቶች ተኮልኵለዋል። እኛ በውጭ በውርጭ ስንገላታ፣ እነሱ ከውስጥ በሙቀት ይቀልጣሉ። “በገዛ ዳቦዬ ልብ ልቡን አጣሁት” ይሉሀል ይኸ ነው! የወያኔ አሽከሮች የአባ ደንገጡሮች ከሆኑ በዙ ወራት አስቆጥረዋል። ወያኔ አዲስ አበባ ላይ በኢቲቪ የወሸከተውን ድራማ፣ ወያኔ ያቆመላቸው እንዳለ ሆዬም እዚህ የራሱን ተመሳሳይ ቅንበር አዘጋጀ። የወያኔን ኢቲቭ ተከትለው፣ “የለንደን ደብረ-ጽዮንን ቅድስት ማርያም ቤተክርስትያን ካኅናት ነን ብለው አይናቸውን በጨው አጥበው የውሸት ጋጋታቸውን በፊልም አቅናብረው አግተውናል። በሕገ-ወጥ መንገድ ቤተክርስትያኗን ያያዙት የወያኔ አጋዦቻቸው ሰተት ብለው ከሥላሴና ከገብርኤል ተጠራርተው መክርቸማቸው ሲገርመን፣ የወያኔን ቴሌቪዥን ዋቢ በማድረግ፣ዘጋቢ ፊልም ሠርተው ሁላችንንም በጅምላው የገንቦት ሰባት አባላት አድርገውን አርፈውታል። የግንቦት ሰባት አባል መሆን እንሱን የሌሊት ቅዥት ሁኖ ያባንናቸው እንደሆን እንጂ፣ ለኛስ ምናችንም አይደለም። እርግጥ የግንቦት ሰባት ስም ሲነሳ እንሱን እሬት-እሬት ሊላቸው ይችላል።ወንድማችን አንዳርጋቸው ጽጌ በሕገ-ውጥ መንገዱ መጠለፉን ለመሸዋወድ ወያኔ ያቀነባበረችውን ተንቀሳቅሽ ፊልም እንደመረጃ ተጠቅመው ስም ማጥፋት የተሳካላቸው መስሎአቸው፣ በዙ-ብዙ ብዙ ነገር ወሽክተዋል። እንዲመሩን የመረጥናቸውን ሰዎች በሙሉ በጅምላው “የግንቦት ሰባት አባላት” ብለዋቸዋል።

አባ ተባዩ፣አንዴ ከዚህ፣ አንዴ ከዚያ ናቸው። በቅንጅት ጊዜ ከቅንጅትም ቅንጅት ነበሩ። አብረው እላይ እታች ብለዋል። ለቶኒ ብሌር ሰላማዊውን ሰልፈኛ፣ ደብዳቤ ካስገቡት መሀል ነበር። አንዳርጋቸው ጽጌ ሽርካቸው ነበር። ዶር ብርሀኑ ጀግናቸው ነበር። ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ለንደንን ስትጎበኝ አባተና እሳቸው፣ ለምነው የመታሰቢያ ፎቶ ተነስተዋል። ከሁለት ዓመት በፊት የወልድባ ገዳም ወያኔ ስትመዘበር፣ አባተና ግሩም አደባባይ ወጥተው ላንቃቸው እስኪነቃ፣ ወያኔን አውግዘዋል[v]። ያንን ሁሉ ያመቻቸላቸው፣ ዛሬ ፖሊቲከኞች፣ ግንቦት ሰባቶች እያሉ የሚያብጠለጥሉት ሕብረትሰብ ነው። ምነው ያኔ ግንቦት ሰባትነታቸው አልታያቸውም? ምነው ያኔ የደርግ መኰንኖች መሆናችን አልታያቸውም? ምነው ያኔ የቅንጀት አባላት መሆናችን አልታያቸውም? ለመሆኑ እንደዚያ ወያኔን ያኔ ሲያወግዙ፣ ካህን ነበሩ ወይስ ፖሊቲከኛ። አሁንስ በትከሻው ላይ ቢሸከማቸው የሚወድ ሕዝብን እንደዚያ ሲያሳዝኑ፣ ከፖሊቲካ ተገልለው ካኅን ሆኑ? በመጀመሪያ ያልተካነ ካህን የለም። ከህነቱን መቀባላቸውንም መረጃ የለንም። አለበለዚያ እንዴት ለንደን መጥተው ቅዳሴን ተማሩ? ጋኖች አለቁና ምንቸቶች ጋን ሆኑ!

ከኛ ሲለዩ ወዴቱ ሄዱ? ወደ ገዳም? የለም! ትላንት ያወግዙት ወደ ነበረው፣ ወደ ወያኔ ጎራ ነው የነጎዱት። ያ ካህን ያስብላቸዋል? ምናልባት “ልማታዊ ካኅን!” ፖሊቲካውን ትተው እኛን ፖሊቲከኞች ቢሉን ባማረማቸው! ከላይ ፎቶአቸውን የምታዮአቸው ወጣት ሴቶችና ወንዶችአሽቃባጮቻቸው “አባ ወያኔ አይደሉም” ሲሉን ከረሙ።ገድላቸውን ሲዘምሩላቸው ሰንበቱ። እራሳቸውንም “የአባቶች እርስት ጠባቂዎች” ብለው አክሌሲያ ነን አሉ። አባ ተባዩ፣ ሕዝባችን የተዋረደበትን ግንቦት ፳ን ሊያከብሩ ወያኔ እምባሲ ዓይናቸውን በጨው ታጥበው ተገኙ።ልብሱን ለበሱት! መስቀሉን ያዙት። አሁን የሚሠሩት ፖሊቲካ አይስብላቸውም ብሎ የሚከራከረን ካለ፣ እሺ ግን ካኅን አይደሉም ነው የምንለው።የሚከተለው ፎቶግራፍ አፍ አውጥቶ ይናገራል [vi]።

የካኅንነቱን መሥፈርት ካየን፣ በተግባር፣ “አባ ግርማ” እንኳን ካህንነት፣ ሽታውም ሽው አላለባቸውም። እግዚአቤሔር ከእንዲህ ዓይነቱ ራስፑቲን ይሰውራችሁ።

የወያኔያዊ ዘጋቢ ፊልም ዓላማ

ዓላማው ግልጽ ነው። አንዳርጋቸው በሕገ-ወጥ መንገድ በወያኔ ተጠልፏል። እነ እንዳለ ወንዳፍራሽ፣ “እያንዳንድሽ እንደዚህ እየተለቀምሽ ትወሰጂያለሽ” እያሉ ይዝቱብናል። ግንቦት ሰባትን ጌቶቻቸው አውግዘዋልና፣ ግንብቶ ሰባት ስንባል፣ የምንሸማቀቅላቸው መስሎአቸው ነው የሚፈራገጡት።

ከመሀከላችን ሻለቃ ማሞ የተባሉ፣ የቤተክርስቲያኗ ምሰሶ የሆኑ ምዕምን አሉ። ሻለቃ ማሞ ወያኔን ሲያደሙ የነበሩ የጦር ሜዳ መኰንን ናቸው። የወጣላቸው ደራሲም ናቸው። “የወገን ጦር ትዝታህዬ” የሚል መጽሐፍ ያበረክቱልን ጸሕፊ ናቸው። እንግዲህ የወያኔ ልማታዊ ካኅናት፣ በሕግ በኩል ሂደው ማሸነፍ ስለማይችሉ፣ ሕገ ወጥ መንገድ መረጡ። ከሕግ ይልቅ፣ አሉባልታ ሕብረተ-ሰቡ መሀል በመዝራት ሻለቃ ማሞን ከግንቦት ሰባት ጋር በማገናኘት አሻማቀው አስበርግገው ከቤተክርስቲያኗ ግቢ የሚያስጠፏቸው መስሎአቸው ነው ይኸን ሁሉ ርቀት የሄዱት። ከንቱ ልፋት!

አንድ አበበ ወንድማገኝ የሚባል ወንድም ቤተሰቡን ለመጠየቅ ኢትዮጵያ ይኸዳል። ምንም ዓይነትፖሊቲካ ውስጥ ገብቶ የሚያውቅ፣ ሰው አይደለም። ስለዚህ ሰው፣ የሰማሁት ወያኔና የ”አባ” ደንገጡሮች ዘጋቢ ፊልሞቻቸው ሲያሰራጩ ነበር። ሻለቃ ማሞን ለማሸማቀቅ፣ የወያኔ ቴሌቪዥን፣ ፈንጂ እንዲያፈነዳ እንዳሰለጠኑት ተናገረ ብለው አቀረቡ። የኛዎቹ የወያኔ ቡችሎች፣ ያንን ይዘው የራሳቸውን ዘጋቢ ፊልም ሠሩበት። ሻለቃ ማሞ፣እንኳን አበበ ወንድማገኝንሊያሰላጡኑትና ከሱ ጋር ተቀምጠው ቁም-ነገርም አውርተው አያውቁም። የወያኔ ነገር ሁሉ በውሸት ላይ የተገነባ ነው። ለመሆኑ እንዲያው አንድ ጥያቄ ለወያኔዎች ላቅርብ። ግንቦት ሰባት አስታጥቆ፣ አስልጥኖ እናንተን የሚያሸብር መላክ ከቻለ፣ የናንተ መሪዎች ወደተሰባሰቡበት ወደ አራት ኪሎ ነው እንጂ ምን አድረገኝ ብሎ ነው ቦምብ አፈንጂ ኃይል ቦሌ መድኃኔዓለም የሚልከው? ስትዋሹም ትንሽ ትንሽ ማስመሰል የአባት ነው! እዲያ ምኖቹ ዓይን አውጣዎች አጋጠሙንጃል!ጋን አስመሳይ ምንቸት ድሮም እንዲሁ ነው።

እንግዲህ የዘጋቢ ፊልሙ ዓላማ፣ በሕግ ሊነጥቁን ያላቻሉትን፣ ግንቦት 7 ናቸው ሲሉን፣ በርግገን የምንተው መስሎአቸው ነው። ትርኪ-ምርኪ ዝባ-ዝንኪ የገበያ ጌሾ! በነገራችን ላይ በክርክራችን ወሳኝ ቦታ ላይ ደርሰናል። ቻሪቲ ኮሚሺን እነዚህ ቀማኞች ትረስቲም እንዳልሆኑ፣ ለሚጥይቃቸውም ጥያቄ መልስ ለመስጠት ፈቃደኛ እንዳልሆኑ፣ እኛ ወደፍርድ ቤት ብንሄድ የሚፈቅድ መሆኑና፤ ኮሚሺኑ የራሱን ምርመራ የሚያካሄድ መሆኑን ውሳኔ ላይ ደርሷል። ደብዳቢውንም የሚከተለው ድረ-ገጽ ላይ ማንባብ ይቻላል። http://londondebretsion.org/wp-content/uploads/2014/09/Charity-commission-response-28Aug14.pdf ይቁርጥ ቀን ደርሷልና በዓለም ዙሪያ የተበተናችሁ ወገኖች ከጎናችን ቁሙ እያልን ጥሪ እናስተላልፋለን።

ድል የእግዚአብሔር ነው!

[i] https://www.youtube.com/watch?v=otlM6x8mzWk

[ii] http://ecadforum.com/Amharic/archives/9750/

[iii] http://www.tigraionline.com/articles/wondemu-mekonen-cadre.html

[iv] http://ecadforum.com/Amharic/archives/12972/

[v] http://www.youtube.com/watch?v=e5dhKLk0Nzc&feature=share

[vi] http://www.ethioembassy.org.uk/news_archive/Ginbot-20_celebrated_in_London.pdf

Hiber Radio: መምህር ግርማ ወደ አሜሪካ ሊመጡ ነው ተባለ፤ ኢትዮጵያ በኢቦላ ይጠቃሉ ከተባሉ አስር አገሮች ተርታ መሰለፉዋ ተገለጸ

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


ህብር ሬዲዮ መስከረም 11 ቀን 2007 ፕሮግራም

እንኳን ለህብር ሬዲዮ አምስተኛ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!

<... ...>

ዶ/ር ኑሩ ደደፎ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር( በጄ/ል ከማል ገልቹ የሚመራው) ቃል የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴና የኢንፎርሜሽን ጉዳይ ሀላፊ ስኮትላንዳውያን የሰጡትን የአንድነት ይሻላል ውሳኔ መሰረት በማድረግ ጠይቀናቸው ለህብር ሬዲዮ ከሰጡን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

<... ...>>

አቶ ግሩምጌታ ዘላለም በስዊድን የኢትዮጵያ ድምጽ ሬዲዮ አዘጋጆች አንዱ ስለ ቅዳሜው ማታ ጠንካራ የኢትዮጵያውያን ተቃውሞ አስመልክቶ ካደረግንለት ቃለ ምልልስ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

የስኮትላንድ ሕዝበ ውሳኔኛ የዓለም ታላላቅ መሪዎች አስተያየት ስለ አንድነት (ልዩ ዘገባ)

(ልዩ ዘገባ)

ዜናዎቻችን

የጋምቤላ ንቅናቄ አገዛዙ ሰሞኑን በመዠንገር ብሄር አባላት ላይ ለፈጸመው ግድአ የበቀል እርምጃ እወስዳለሁ አለ

ኢትዮጵያ ዛሬም በኢቦላ ይጠቃሉ ከተባሉ አስር አገሮች ተርታ መሰለፉዋ ተገለጸ

በስዊድን ኢትዮጵያውያን በአገዛዙ አምባሳደርና አጃቢዎቻቸው ላይ የተበላሸ ዕንቁላልና አሳ በመወርወር ተቃውሟቸውን ገለጹ

መምህር ግርማ ወደ አሜሪካ ሊመጡ ነው ተባለ

መኢአድ አንድ አባሉ ሰሞኑን በወያኔ በጥይት ተደብድበው መገደላቸውን ገለጸ

የእንግሊዝ ፖሊሶች በአገሪቱ ከወራት በፊት ህገወጥ የሆነውን ጫት ሰሞኑን ያዙ

የተመድ የአገዛዙን በጸረ ሽብር ሕግ ስም የሚወስደውን የአፈና እርምጃ እንዲያቆም ጠየቀ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

ኢህአዴግ የሰራው ቤት! ግድግዳው ሰንበሌጥ!

$
0
0

ገለታው ዘለቀ

እንደ መግቢያ
ፌደራሊዝም የመንግስት ኣወቃቀር ሰፊ የቆዳ ስፋትና ብዙ ህዝብ ላላቸው ኣገሮች፣ በዛ ያሉ የተለያየ ቋንቋና ባህል ያላቸው ቡድኖች ላላቸው ሃገሮች፣ ተመራጭ ኣስተዳደራዊ መዋቅር እንደሆነ እጅግ ብዙ ሰው በዓለም ላይ ይስማማል። ፌደራሊዝም የተመረጠበት ዋናው ምክንያት ስልጣን እና ፍትህ ከህዝቡ እንዳይርቅ ነው። እንዳይርቅ ስንል ከመልክዓ ምድርም ከወረፋም ኣንጻር ነው። ትላልቅ የሆኑ ኣገሮች ስልጣንን ቢያማክሉ ዜጎች ለኣንዳንድ ጉዳዮች ስልጣን ወደተጠራቀመበት ለመሄድ ስለሚርቃቸው ብዙ ከሆኑ ደግሞ ሰልፉ ስለሚበዛ ወረፋው መጉላላትን ስለሚፈጥር ነው። ዜጎች ስልጣን ወርዶ ከፍተኛ የሆኑ ጉዳዮቻቸውን ሳይቀር በክልሎቻቸው እንዲታይላቸው መደረጉ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን ፍትህንና ኣገልግሎትን ለማደል በጣም ይረዳል። ስልጣን ተማክሎ የመካከለኛና ዝቅተኛ ደረጃ ባለስልጣናት እንደ ቧንቧ ማስተላለፍ ብቻ ከሆነ ስራቸው መንግስትና ህዝብ ልብ ለልብ ከመራራቃቸውም በላይ በውሳኔና በእቅድ ላይ ተሳትፎኣቸው ዝቅተኛ ይሆናል ኣገልግሎት ኣሰጣጡም ብዙ ችግር ይገጥመዋል።። ሌላው ደግሞ የተለያየ ባህልና ቋንቋ ያላቸው ቡድኖች በተለያየ መልክዓ ምድር ለብቻ ለብቻ ሰፍረው ነገር ግን ደግሞ ኣንድ ኣገር መስርተው እየኖሩ ከሆነ እንዲሁ ባንድ በኩል ባህላቸውንና ቋንቋቸውን ጠብቀው በኣንድ ሃገር ጥላ ስር እንዲኖሩ የሚረዳ መሆኑንም ሁሉም ይረዳል። ኢትዮጵያ ካላት የቆዳ ስፋትና ካላት የህዝብ ብዛት እንዲሁም ካላት የቡድኖች ብዛት ኣንጻር ፌደራሊዝም ተመራጭ ኣስተዳደር መሆኑን እጅግ ብዙ ሰው ያምናልና በዚህ ላይ ውይይት ኣስፈላጊ ኣይደለም።

eprdfበዚህች በዛሬዋ መጣጥፌ የማስተላልፈው መልእክት ፌደራሊዝም ጠቃሚነቱን ለመግለጽ ሳይሆን ኣቶ መለስ ዲዛይን ኣደረጉት ወይም በሳቸው ምህንድስና ተዋቀረ የተባለውን የዛሬይቱን ኢትዮጵያን የፌደራል ኣወቃቀር ትንሽ መተቸት እፈልጋለሁ። መተቸትም ብቻ ሳይሆን ምን ኣልባት ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ሊጠቀሙበት ይችሉ ይሆናል በሚል ተስፋ ኣማራጭ የፌደራል ኣወቃቀር ኣሳብ ለማቀበል እሞክራለሁ።

የኢትዮጵያ የፌደራል ስርዓት

የኢትዮጵያ ፌደራል ሲስተም ተፈጥሮ በሚገባ ከሚገለጽባቸው ጉዳዮች መካከል ኣንዱ የክልሎች መንግስታት ኣወቃቀር ነው። እነዚህ መንግስታት ሲዋቀሩ መስፈርቱ ምን ምን እንደሆነ ማወቅ የኢትዮጵያን ፌዴራል ስርዓት ለመረዳትና ለመገምገም ይጠቅማል። ኣቶ መለስ ዲዛይን ያደረጉትን ይህንን የክልል ኣፈጻጸም ብዙ ሰው የሚገልጸው በብሄር ፌደራሊዝም(Ethnic federalism) ነው። በርግጥም የፖለቲካውን ኣወቃቀር ስናይ ማለትም የፖለቲካው እግሮች(radicals) በብሄር ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ፌደራሊዝም ካለ የብሄር ፌደራሊዝም ነው ያለው ለማለት ያስችለናል። ይሁን እንጂ የክልል መንግስታቱ ኣመሰራረት በምን ላይ እንደቆመ ማየት ደግሞ የመንግስትን ተፈጥሮና ፍላጎት ለማየት ይረዳናል። ስለዚህ የነዚህ የዘጠኝ ክልሎች መንግስታት ምስረታ ይህንን የብሄር ፌደራሊዝም የተባለውን መርህ ተከትሎ ነው ወይ የተፈጸመው ብለን ማየት ተገቢ ነው። የገዢው መንግስት ኣካላትና ደጋፊዎቻቸው እንደሚገልጹት የክልል መንግስታት ምስረታው ራስን በራስ ማስተዳደርን መሰረት ያደረገ፣ ማንነትን ያገናዘበ፣ የብሄር ብሄረሰቦችን መብት ያገናዘበ እንደሆነ በኣጠቃላይም በብሄር ፌደራሊዝም(Ethnic federalism) ሊገለጽ እንደሚችል ይስማማሉ።

የብሄር ፌደራሊዝም በምሁራንና በኣብዛኛው ህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ነቀፌታ ያለበት ቢሆንም መንግስት ግን በተለይ የብሄር ብሄረሰቦችን “ራስን በራስ የማስተዳደር መብትን” እንዳጎናጸፈለት ደጋግሞ ይገልጻል። ኣጥብቀው ለሚቃወሙት ወገኖች ደግሞ የብሄር ፌደራሊዝም እኛ ጋር ብቻ ኣይደለም ያለው ስዊዘርላንድን፣ ህንድን፣ ቤልጂየምን ተመልከቱ እነሱም በብሄር ላይ የተመሰረተ ፌደራሊዝም ነው ያላቸው ይላል። በመሰረቱ ግን የነዚህን ኣገሮች ኣወቃቀር በሚገባ ማየት ያስፈልግ ይመስለኛል። ርግጥ ነው ስዊዘርላንድ ምንም እንኳን የህዝብ ብዛቱዋ ትንሽ ቢሆንም ጀርመንኛ ተናጋሪዎችን፣ ጣሊያንኛ ተናጋሪዎችን፣ፈረንሳይኛ ተናጋሪዎችንና ሪሂቶ ሮማንስን በሃያ ስድስት ካንቶኖች ከፋፍላ በባህላዊ ኣስተዳደር እያስተዳደረች ያለች ኣገር ናት። ። ስዊዘርላንድ ውስጥ ያለው ይህ ቋንቋን የተከተለ ኣከላለል ባንድ በኩል ባህልን እየጠበቁ በሌላ በኩል ለኣስተዳደር ኣመቺነቱን በማየት ነው። የስዊዘርላንድ ኣከላለል ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ሳይሆን ኣስተዳደራዊ ኣመቺነትን በማየት ነው። በብሄር በፖለቲካ መደራጀትን የስዊዘርላንድ ህግ ይከለክላል። ከኢትዮጵያ የሚለየው በዚህ ነው። የኢትዮጵያ የክልሎች ኣወቃቀር በብሄር ፖለቲካ ላይ የተመሰረተ ፌደራሊዝሙም የሚመነጨው ከዚህ ኣስተሳሰብ ነው።ዋናው ፍልስፍናቸውም “ብሄሮች ራሳቸውን በራሳቸው ያስተዳድሩ” የሚል ፖለቲካዊ ኣስተዳደርን የሚመለከት በመሆኑ ነው ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ነው የሚያሰኘን። የኢትዮጵያ ፌደራሊዝም ከዚሁ ከብሄር ፖለቲካ ኣስተሳሰብ የመነጨ ሲሆን የስዊዝ ደግሞ በኣንድ ብሄራዊ ፖለቲካዊ ማንነት ጥላ ስር ያደረ ባህላዊ ኣስተዳደር ተደርጎ ነው ሊወሰድ የሚችለው። ስዊዘርላንድ ከላይ እንደ ጥላ የረበበ ኣንድያ ጠንካራ ማንነት ያላት ሲሆን ኢትዮጵያ በኣሁኑ ጊዜ ብሄራዊ ማንነቷ የት እንዳለ የት እንደተጠለለ በሚገባ ኣይታይም። ለዚህም ነው ብዙ ኢትዮጵያዊያን ኢትዮጵያዊነታችንስ? የት ጣላችሁት? ….ወዘተ. እያሉ የሚያጉረመርሙትና ፍለጋ የገቡት:: በኢሕ ኣዴግ ዘመን ኢትዮጵያዊነት የት ኣደረ? የት ነው ያለው? ብለን ኣጥብቀን ከጠየቅን ኢትዮጵያዊነትን ኣድሮ የምናገኘውና ብሄራዊ ማንነት የሚገለጸው በብሄር ፓርቲዎች ግንባር ደረጃ ነው። ኢሕ ኣዴግ ኣይዲዮሎጂ በሌላቸው የብሄር ፓርቲዎች የተገነባ ግንባር ሲሆን የግንባር ተፈጥሮ ደግሞ ለኣንድ ለተወሰነ ዓላማ የሚሰባሰቡበት ድርጅት ነው። በርግጥ ኢሕዓዴግ የሚባለው ራሱ በዓለም ላይ ኣለ ወይ? የሚለውን ፍልስፍናዊ ጥያቄ ለጊዜው ቁጭ ኣርገነው ግንባር የሚመሰረተው ለኣንድ ለተወሰነ ዓላማ ነው። ግንባር የመሰረቱ ድርጅቶች መንግስት የመጣል ተፈጥሮ ካላቸው እስኪጥሉ ኣብረው ይታገሉና ከዚያ በሁዋላ ወይ ይዋሃዳሉ ወይ በየፊናቸው ይቀጥላሉ። ግንባር በተፈጥሮው ኣድራሽ ነው። ዘላለማዊ ኣይደለም። ትልቁ ችግር ግንባር መሆኑ ብቻ ሳይሆን በብሄር ድርጅቶች የተፈጠረ ግንባር መሆኑ ነው። ኢሕ ኣዴግ ስልጣን ሲይዝ ወይም መንግስት ሲመሰርት ይሄው የግንባር ተፈጥሮው ይንጸባረቃል። ኣንቅጽ ሰላሳ ዘጠኝም የዚህ ተፈጥሮ ውጤት ይመስላል። እስከ ተወሰነ ኣብረን ግንባር ፈጥረን እንሄዳለን ካልሆነ እንለያያለን ኣይነት ነው ነገሩ። ብዙ ጊዜ የመንግስት ተወካዮች ኢህዓዴግ ስልጣን ከለቀቀ ኣገሪቱ ትበታተናለች ብለው የሚናገሩትና የሚያምኑት እነሱ የፈጠሩዋት ኢትዮጵያ ብሄራዊ ማንነት በግንባር ደረጃ ተውሸልሽሎ ያለ በመሆኑ ይሄው እየታያቸው ሊሆን ይችላል። ስዊዘርላንድ ምንም እንኳን ክልል የሰራችው በቋንቋና በባህል ላይ ቢሆንም ፖለቲካዊ ጨዋታዋ ግን በኣንድ ጠንካራ የፖለቲካ ማንነት ጥላ ስር ነው። ይህን ብሄራዊ ማንነት ትቶ በብሄር ማንነት ላይ የፖለቲካ ቤት መስራትና የጀርመንኛ ተናጋሪዎች የፖለቲካ ድርጅት የፈረንሳይኛ ተናጋሪዎች ድርጅት የሚባል ነገር በህግ ክልክል ነው።ግንባር ነኝ የሚለው ኢህዓዴግ ኢትዮጵያን በግንባር የፖለቲካ ኣስተሳሰብ የሚያስተዳደር ሲሆን እስከ መቼ ለሚለው ጥያቄ መልሱ ኣይታወቅም።ይህ ኣንቀጽ ሰላሳ ዘጠኝ ለማስፈራሪያ ተቀምጦም ከሆነ ማንን ለማስፈራራት እንደተቀመጠም ኣይታወቅም። ጉዳዩ በማስፈራራት ወይም ካልሆነ እንለያያለን ብለን ሰለጻፍን ዋስትና ኣይሆነንም።
EPRDF
የዚህ ዘመን ኣስተዳደራዊ ችግር የሚመነጨው ከፖለቲካው የመጀመሪያ የእምነት ምንጭ ነው። በመጀመሪያ ደረጃ የብሄር ፖለቲካ እምነት ዋናው መነሻ ስነ -ህይወታዊ (DNA and genealogy)ጉዳይን ኣጥብቆ የያዘ መሆኑ ነው። በዚህ ኣሳብ ልብ ውስጥ ያለው ጉዳይ ኣንድ ሰው ኣገር ለሚለው ጽንሰ ሃሳብ ማሰብ ሲጀምር ከታች እንዲጀምር ነው የሚበረታታው። ቤተሰብ፣ ዘመድ ኣዝማድ፣ ጎሳ፣ ብሄር ከዚያ ኣገር እያለ ከታች ወደ ላይ የሚሄድ እምነት ነው። የህወሃት ሰዎች የደም ጉዳይ ነው…… ተፈጥሮ ነው…… ምን እናድርገው? ይላሉ።እርግጥ ነው ስነ-ተፈጥሮኣዊ እውነት ኣለ። ኣንድ ሰው ለቤተሰቡ ማለትም ለወንድሙ፣ ለእህቱ፣ ለናቱ፣ ላባቱ ወዘተ. የሚራራና የሚታመን ቅርብ ልብ ኣለው። ከዚያም ከፍ ሲል ለዘመዶቹ ከዚያም ባህል ኣቋራጭ (cross cultural) ጉዳይ ሲመጣ ለባህላዊ ቡድኑ ተቆርቋሪ መሆኑ ተፈጥሮኣዊና ስነ-ተፈጥሮኣዊ ሊሆን ይችላል።ይሄ ኣይካድም። የብሄር ፖለቲካ ይህንን ስነ ህይወታዊ ትንታኔ ይዞ ነው ፖለቲካዊ ይዘት ያለበሰው። ከዚህ ጽኑ የጄነቲክ እምነቱ የተነሳም ብሄሮች በራሳቸው ባህላዊ ቡድን ኣባል ኣስተዳደራዊ መዋቅር ቢዘረጉ ኣስተዳደሩ ርህራሄ ይሞላዋል፣ ችግርን መረዳት ይኖራል፣ ከፍተኛ ተግባቦት ይኖራል፣ ስለዚህ በተወላጁ መተዳደሩ ተፈጥሮኣዊ መሰረት ያለው ነው የሚል እምነት ያለ ይመስላል።ይሄ መሰረታዊ የብሄር ፖለቲካ ፍልስፍና በርግጥ ገዢውን መንግስት ኣብከንክኖታል ወይ? የሚለውን እንተወውና በኣጠቃላይ የብሄር ፖለቲካ እምነት ምንጩ እንደዚያ ነው። የዚህ የብሄር ፖለቲካ መሰረታዊ እምነት ግን ትልቅ ችግር ያለበት ነው። ችግሩ ምንድነው? ካልን የዴሞክራሲና የፍትህ ተፈጥሮ ከዚህ መሰረታዊ እምነት ጋር ኣብሮ ኣለመሄዱ ነው። ዴሞክራሲና ፍትህ ከላይ ሆነው ነው የምናያቸው። ፍትህና ዴሞክራሲ መርህ ነው ወገናቸው። ጀነቲክ ወይም የደም ሃረግ ጉዳይ ዓይደለም። ዴሞክራሲ ኣስተዳደሩን ሲዘረጋ በብዙሃን ድምጽ ከላይ ይነሳና ወደ ታች እስከ ግለሰብ ድረስ ወርዶ፣ የልዩነት የመጨረሻው ቅንጣት እስከ ሆነው የግለሰቦች የተለያየ ተሰጥዖ፣ችሎታና ምርጫ ድረስ ወርዶ እንክብካቤ የሚያደርግ ስርዓት ነው። እነዚህ ሁለት የሃገር ዋልታና ማገሮች ማለትም ፍትህና ዴሞክራሲ ከዚያ ከብሄር ፖለቲካ ጋር የሚጻረሩት በዚህ ነው። ኣንዳንዴ ወንድምህና ኣንድ የማታውቀው ሰው በፍትህ ፊት በዴሞክራሲ ፊት ቆመው ሳለ ወንድምህ ካጠፋ በወንድምህ ላይ ትፈርድ ዘንድ ያስገድድህና የባዮሎጂውን የርህራሄ የምናምኑን ጉዳይ ይሰብረዋል። የጀነቲኩን ጉዳይ ኣደባባይ ላይ ሳያወጣ ግለሰባዊ ኣድርጎት ቁጭ ይላል። በመሆኑም ዴሞክራት መሪዎች በኣስተዳደር ጊዜ ከላይ ይሆኑና የተፈጥሮ ሃላፊነታቸውን ከዘመዶቻቸው ጋር የሚወጡት በጓዳ ነው። ንስር በተፈጥሮው ከፍ ብሎ ይበራል። ከፍ ብሎ እየበረረ ወደ መሬት ጥቃቅን የሆኑ ነገሮችን ነጥሎ የማየት ችሎታ ኣለው። ዴሞክራት መሪዎች የዴሞክራሲንና የፍትህን መርሆዎች ከላይ ይዘው ታች የግለሰቦችን ህይወት የሚነካ ስራ ይሰራሉ። የብሄር ፖለቲካ መሪዎች ደግሞ ጄነቲክ የሆነውን ተፈጥሮኣዊ የጓዳ ግንኙነት የፖለቲካ ቤት ሰርተው ኣደባባይ ኣውጥተው ደግሞ በሌላ በኩል ዴሞክራሲን በሌላ እጃቸው ለመጎተት ሲሞክሩ ይታያል። በኢትዮጵያ ውስጥ ኣሁን ያለው ግጭት ይሄ ነው። የዚህ የብሄር ፖለቲካ ኤነርጂ ለዴሞክራሲ ያልተመቸውም በዚህ ነው። በእንዲህ ዓይነት መሬት ላይ ዴሞክራሲ ቢዘራ ኣይበቅልም። የዴሞክራሲና የብሄር ፖለቲካ ተፈጥሮ ኣብሮ ባለመሄዱ ነው ዛሬ ዴሞክራሲ በሃገራችን የጠፋው። ከፍ ሲል እንዳልኩት የህወሓትና የሌሎች ብሄር ተኮር ድርጅቶች ችግር የእምነት ችግር ነው። ይህ እምነት ደግሞ ባዮሎጂካዊ እውነት ቢኖረውም ኣስተዳደራዊና ፖለቲካዊ መልክ ሲይዝ ጥሩ ኣይደለም። የብሄር ፖለቲካ በዓለም ታሪክ ውስጥ ብዙ ኪሳራ ኣምጥቱዋል።የብሄር ፖለቲካ ኣራማጆች ካደጉበት መንደር ወጥተው ኢትዮጵያን በሙሉ ዓይን ማየት መጀመር ካልቻሉ የኢትዮጵያን ኣንድነት መረዳት ያዳግታቸዋል። ታላቋ የሰብአዊ መብት ተሟጋች የተባበሩት ህዝቦች የስደተኞች ድርጅት (UNHCR) መልካም ፈቃድ ኣምባሳደርና የፊልም ተዋናይ ኣንጀሊና ጆሊ በኣንድ ወቅት የተናገረችውን ቁምነገር እዚህ ጋር መጥቀስ ኣስፈላጊ ይመስለኛል።

“If you don’t get out of the box you’ve been raised in, you won’t understand how much bigger the world is” Angelina Jolie

eprdf_meetingሌላው የዚህ የፌደራሊዝም ምህንድስና ጉዳይ ሲነሳ የኢትዮጵያን ኢሜጅ የማስተካከልም ስራ ነው። የኢትዮጵያን ብዙነትና ኣንድነት ማሳየት የሚችል የፌደራል ስርዓት ያስፈልጋል። የኣሁኑን ስርዓት ስናይ ኢትዮጵያን የሚገዛት የብሄር ፖለቲካ መሆኑ ብቻ ሳይሆን የሚያሳዝነው የብሄር ፖለቲካው ኣምባገነን መሆኑ ነው። በዚያው በብሄር ከተደራጁት መካከል ኣንዱ ሲበዛ ሃይለኛ ሆኖ በኣምባገነንነት ይኖራል። ለስሙ የብሄር ጉዳይ ይግነን እንጂ ኣንድ ሃይለኛ ፓርቲ በየቡድኑ የተወከሉትን ኣስተዳዳሪዎች የሚቆጣጠርበት እንደፈለገ የሚያደርግበት ሁኔታ በመሆኑ ስልጣን በተግባር ያለ ልክ ተማክሎ ነው የሚታየው። ይሄ ችግርም የዚሁ የብሄር ፖለቲካ ተጽእኖ መገለጫ ነው። እንደዚህ ዓይነቱ ፖለቲካ ባለበት ምድር ዳይቨርስ የሆኑ ከተሞች እንደ ኣዲስ ኣበባና ሌሎች ከተሞች ችግር ውስጥ ይገባሉ። ኣጠቃላይ የሆነው ኣስተሳሰብ ቢያንስ ወደ ማንነት ድምጽ(Identity Voting) ሊመራቸው ይችላልና በምርጫዎች ላይ ጥላ መጣሉ ኣይቀርም።ኣንድ ሰው ኣዲስ ኣበባ እየኖረ በመታወቂያው ላይ ኣማራ… ትግሬ…. እየተባለ መጻፉ የዚህ ኣስተሳሰብ ውጤት ነው። ፓለቲካው ኣስተዳደራዊ ጉዳይን ከማንነት ጋር ስለጨፈለቀው የፖለቲካ ሰዎች ለምርጫ ሲቀርቡ የብሄር ዳራቸውን የማወቅ ፍላጎት በዜጎች ዘንድ ከማደሩም በላይ ከተመራጩ ታለንትና ፖለቲካዊ ብቃት ይልቅ ለጄነቲክ ጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ ስለሚገፋ ዜጎች ለማንነት ድምጽ(identity voting) መጋለጣቸው ኣይቀርም ከዚያም ጋር ተያይዞ ለሚመጣ ሃሜትና ጉምጉምታ መጋለጣቸውም ኣይቀርም በውጤቱም ኣጠቃላይ የዴሞክራሲን ባህል እያጠፋ ይሄዳል።የህዝቡን ስነ ልቦናም ያበላሻል።ኣክቲቪስቶች ሳናውቀው የዚህ ፖለቲካ ሰለባ እንዳንሆን መጠንቀቅ ኣለብን። ሳናውቀው ሰለባ ከሆንን ኣዲስ ኣበባ ኣካባቢ ሁለት ሰው ሲሞት የምንጮኸውን ያህል ኦጋዴን ወይም ጋምቤላ በጅምላ ሲጨፈጨፉ ኣዘናችን ያን ያህል ላይሆን ይችላል።
የብሄር ፖለቲካ ችግሩ የመነሻው እምነት ነው ብለናል።ዴሞክራሲስ እምነት ኣይደለም ወይ? የሚል ጥያቄ ይነሳል።በርግጥ ዴሞክራሲ ይልቃል ስንልም በእምነት ነው። በዴሞክራሲ ላይ ስንቆምም በዴሞክራሲ ላይ ታምነን ነው። ልዩነቱ ዴሞክራሲ በተፈጥሮው የቆመበት መሰረት ከጄነቲክ፣ ከባህልና ቋንቋ መሰረት በላይ በሰው ግለሰባዊ ስብእናና ታለንት ላይ በመታመን ፍትህን ማደል ሲሆን በጋራ ምርጫ ጊዜ ደግሞ ኣንድ ሰው ለኣንድ ድምጽን መሰረት ያደረገ ነጻ ምርጫ ኣድርጎ በድምሩ ኣብላጫ ያለውን ድምጽ ኣሸናፊ በማድረግ ተሸናፊው የኣሸናፊውን ድምጽ ኣክብሮ በጋራ እስከ ቀጣዩ ምርጫ መስራት ነው። ዴሞክራሲ ከላይ ሆኖ የሚያይ በመሆኑ በዚህ ጥላ ስር ዜጎች ቢያርፉ እረፍትና መተማመን ሊያመጣላቸው ይችላል የሚል እምነት ነው ያለው። ይህ እምነት ደግሞ በተግባር ተፈትኖ የወጣለት በመሆኑ ነው የምንመርጠው። ከሁሉም በላይ ከዘመኑ የሰው ልጆች ኣስተሳሰብ ደረጃ ጋር ኣብሮ መጓዝ የቻለ የኣስተዳደር ጥበብ ሆኖ በመገኘቱ ነው ይህን እምነት የበለጠ እንድናምነው የሚያደርገን። ሌላው ከፍ ሲል እንዳልነው የዚህ የብሄር ፖለቲካ እምነት የፍትህ ኣሳላፊዎቹን ብሄራዊ ማንነት ለማወቅ በፍትህና ኣገልግሎት ፈላጊዎች ዘንድ ፍላጎት እንዲሰርጽ ማድረጉ ነው። በዴሞክራሲ ጊዜ ይህ ስሜት ጨርሶ ይጠፋል ማለት ኣይደለም። ይሁን እንጂ ከላይ ያለው የዴሞክራሲ መርህ ለዜጎች መተማመኛ ስለሆነ በኣንዳንድ ሰዎች ስሜት ላይ ሊጎላ የሚችለውን ችግር ተጠያቂነት የሚባለው ነገር ስላለ ይህንን ስሜት ያደበዝዘዋል፣ ቀስ እያለ ዴሞክራሲ ባህል እየሆነ ሲመጣ ደግሞ ይህ ስሜት እየከሰመ ይሄዳል።የኢትዮጵያን ኢሜጅ ስናስብ የኣንድ ብሄር የበላይነት የነበረባት ኣገር ከነበረች ኣሁን ደግሞ የበለጠ ስም ኣውጥቶ የሌላ ኣንድ ብሄር የበላይነት ካለ ለውጥ የለም። የኢትዮጵያ ኢሜጅ የሚስተካከለው በዴሞክራሲና በፍትህ ነው። ዜጎች እንደ ዜጋ ቡድኖች እንደ ቡድን እኩል ሲሆኑ የቡድኖች ትንሽና ትልቅነት ሲጠፋ ፍትህ ሲበየን የሃገሪቱ ኢሜጅ ይስተካከላል። መቶ የፖለቲካ ፓርቲ በየስማችን ማቋቋሙ የኢትዮጵያን ኢሜጅ ኣያሳይም። ካሳየም የተበታተነች ኣገር መሆኑዋን ነው። ባህላዊ ማንነትንና ፖለቲካዊ ማንነትን መለየት ያስፈልጋል ። ብዙ ኣገሮች እምነትንና ኣስተዳደርን ለይተው ይታያል። በኢትዮጵያ ህገ መንግስትም ኣንቀጽ ኣስራ ኣንድ ላይ ሃይማኖትና መንግስት መለያየታቸውን ይገልጻል። ልክ እንደዚህ ኢትዮጵያ ባህላዊ ማንነትንና ፖለቲካዊ ማንነትን መለየት ኣለባት ለዚህም ኣንቀጽ ኣስራ ሁለት ብላ እነዚህ ጉዳዮች መለያየታቸውን ማስመር ኣለባት።

መጀመሪያ ወደ ኣነሳነው ጉዳይ እንመለስና ለዛሬው የኢትዮጵያ ፌደራሊዝም ሌላዋ የኢህዓዴግ ምሳሌ ደግሞ ህንድ ናት:: እውነት ነው በርግጥ ህንድ ውስጥ የክልል ፓርቲዎች ኣሉ:: ኢትዮጵያ ውስጥ ህወሃት ብዓዴን ወዘተ. እንደሚባለው ህንድም ውስጥ የክልል ወይም(state or local parties) የሚሉዋቸው ፓርቲዎች ኣሉ።። ይሁን እንጂ ስልጣኑን የያዘውና እጅግ ኣብዛኛውን መቀመጫ የተቆጣጠረው ብሄራዊ ኣጀንዳ ያለው በዚህ ኣመት ለጠቅላይ ሚንስትርነት በተመረጡት ናረንድራ ሞዲ የሚመራው BJP የተሰኘው ብሄራዊ ፓርቲ ሲሆን የክልል ፓርቲዎች ተሰሚነታቸው በጣም ዝቅተኛ ነው።በያዝነው ኣመት ህንድ ውስጥ በነበረው ምርጫ ቀደም ባሉት ጊዚያት ከተለያዩ ፓርቲዎች ጋር ውህደት ፈጽሞ ተጠናክሮ የወጣው BJP ፓርቲ ኣምሳ ኣንድ ነጥብ ዘጥኝ በመቶ የሚሆነውን ኣጠቃላይ ምርጫ ያሸነፈ ሲሆን ሌሎች ከፍተኛ መቀመጫ የያዙትም ብሄራዊ ፓርቲዎች ናቸው። የክልል ፓርቲዎች እዚህ ግባ የማይባል ውጤት ነው ያላቸው። በኣጠቃላይ ህንድ በብሄራዊ ፓርቲዎች የመንፈስ ልእልና የምትመራ ኣገር ስትሆን ብሄራዊ ፓርቲ ቢዳከምና የክልል ፓርቲ ቢያብብ በርግጥ ህንድም ኣደጋ ላይ መውደቋ ኣይቀርም። ነገር ግን የሚመስለው ህንዶች የክልል ፓርቲዎችን ለጊዜው ዝም ያሉዋቸው ሲሆን በምርጫ እየቀለሉ ቀስ እያሉ ይጠፋሉ ከሚል ዘዴም ሊሆን ይችላል እንጂ ህንድም ብትሆን የማንነት ፖለቲካን የምታበረታታ ኣገር ኣይደለችም።ማሌዢያን ብናይ በርግጥም በዘር ላይ የተመሰረቱ ወይም ስያሜያቸው ከዘር ጋር የተያያዘ የፖለቲካ ፓርቲዎች ኣሉ። ጠንካራ የሆነ ፓርቲ ቢኖራቸውም በብሄር ላይ የቆሙት ፓርቲዎች የኣድቫንቴጅ ጥያቄዎችን በየጊዜው እንዲያነሱ ያደርጋቸዋል። በህንድና በማሌዢያ የዚህ የብሄር ፖለቲካ ክፉ ውጤት ጎልቶ ካልታየባቸው ጉዳዮች መካከል ኣንዱ የኢኮኖሚው እድገትም ይመስላል። ዜጎች የኢኮኖሚ ሁኔታቸው ሻል ሲል ዘንጋ ቢሉም የኢኮኖሚው ሁኔታ መናጋት ሲጀምር እንደ እምቅ ችግር ሆኖ መነሳቱ ዓይቀርም። በቅርቡ የእስያ ሪቪው እንደዘገበው የማሌዢያ ኢኮኖሚ መውደቅ ሲጀምር ዘረኝነት ብድግ ማለቱን ገልጹዋል። በዘር ላይ የቆመ ፖለቲካ ሲኖርና የሪሶርስ ማነስ ሲሰማን ያ በዘር ላይ የቆመው ፖለቲካ ድርጅት ስልጣኑን ተጠቅሞ ወገኑን ይረዳል ብለን መጠርጠር የመጀመሪያ የዓመጽ መነሻችን እንዲሆን ሊያደርግ ይችላል። የትም ሃገር በብሄር ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ የሚያራምዱ ሁሉ መውጫ ፍለጋ እየጣሩ እንጂ ተደስተው ኣይኖሩም። ብሄራዊ ማንነታቸው ተናግቶ፣ ፍትህ ቀጭጮ ተቸግረው ነው ያሉት።

ቤልጂየምም ብትሆን ከኢትዮጵያ የተለየች ናት። በዘውዳዊ ህገመንግስት (constitutional monarchy) ስር ያሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቢኖሩም ኣንድ ከላይ የረበበ ብሄራዊ ኣንድነት ይዙዋቸው ይታያል። ስለ ህገመንግስታዊ ሞናርኪ ሳስብ ለእኔ የሚመስለኝ፣ ያልተጻፈ ቢሆንም፣ ምንም እንኳን ከዘውዳዊ ኣገዛዝ ወደ ዘመናዊነት መሸጋገር ያማራቸው ኣገሮች ኣዲሱ ትውልድ በኣንድ ወቅት ዘውዳዊ ኣባቱን ኣሁን እኔ ኣዲስ ኣስተዳደር ተገልጦልኛል፣ ዴሞክራሲ በተባለ ጥበብ ኣገሪቱን ላስተዳድር ነው ብሎ ለውጥ ሲጀምር ዘውዳዊ ኣገዛዙን በስምምነት ኣስተዳደራዊ ጉዳዮችን እንዲሰጠው ጠየቀ ማለት ኣዲስ የሚመጣው ኣስተዳደራዊ ስርዓት፣ ዳይናሚክ የሆነው ጥበብ ፣ ሉዓላዊነትን ከዘውዱ ይነጥቃል ማለት ኣይመስለኝም። ዘውዱ ኣሁንም የኣገሪቱን ሰማይና የብስ የሚገዛ ይመስለኛል። ኣልገባኝ እንደሆን ኣላውቅም። ለማናቸውም ግን ዘውዳዊ ኣገዛዙን ያልገደሉ ዘመናዊነት ሲመጣ ወደ ህገ መንግስታዊ ዘውዳዊ ኣገዛዝ ሲመጡ በህገ መንግስት ብዙውን ኣስተዳደራዊ ስልጣን ኣዲስ ነገር ተገልጦልኛል ላለው ትውልድ ቢሰጠውም ልእልናው ግን ኣለና ያ ልእልና የኣንድ ሃገር ብሄራዊ ማንነትን ሊገልጽ የሚችል ከላይ የረበበ ጥላ ሊሆንላቸው ይችላል:: የዳር ድንበርን (territorial integrity) ጉዳይ በህይወት ሆኖ ታሪክን የሚያስታውስ ይመስለኛል። የቤልጂየም ንጉስ ፊሊፕ ኣንድነትን ሲያበረታቱ ነው የምናየው። ይህም የቤልጂየም ዘውድ ለኣንድነታቸው መገለጫ መሆኑን ያሳያል። ኢትዮጵያ በ1960ዎቹ ጊዜ የሆነ ኣዲስ ነገር በራልኝ ያለው ትውልድ ዘውዱን በድንጋይ ስቶ ሲያበቃ ወታደር ሲመጣ በጥይት ብሎ ስለገደለ ብሄራዊ ኣንድነታችንን የምንገልጽበት ምልክት (symbol) በብሄር ፖለቲካ ጊዜ የለንም።

ኔፓል እንደሚታወቀው እንደ ኢትዮጵያ ብዙ የተለያየ ቋንቋና ባህል ያላቸው ቡድኖች የሚኖሩባት ኣገር ናት። ይህቺ ኣገር በ 2008 ዓ.ም ከፍጹም ዘውዳዊ ኣገዛዝ ከተላቀቀች በሁዋላ ኣዲሲቱዋን ኔፓልን በምን መንገድ ኣዋቅረን እንቀጥል የሚለው ጉዳይ እስካሁን ያልተቋጨ የኔፓሊስ ሌሂቃን የቤት ስራ ሆኖ ይታያል። የማኦይስቶች እምነትና ግፊት ኔፓል በብሄር ፌደራሊዝም እንድትተዳደር ሲሆን የኔፓል ኮንግረስ ፓርቲ መሪና የኣሁኑ ጠቅላይ ሚንስትር ሶሺል ኮይራላ ግን ይህን ኣሳብ በጥብቅ እየተቃወሙ ነው። የኔፓል ኮንግረስ ፓርቲ በሃገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ የፖለቲካ መሰረት(constituency) ያለው ሲሆን ይህ ፓርቲ የብሄር ፌደራሊዝም በዓለም ላይ ግጭትን ያመጣ በመሆኑ ኣዲስ ሊፈጥሩት ባሰቡት ህገ መንግስት እንዳይካተት እየወተወቱ ነው።

እንዲህ ዓይነት በማንነት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ ብዙህ በሆኑ ሃገሮች ቀርቶ ሆሞ ጂኒየስ በሆኑ ኣገሮችም እንኳን ጥሩ ኣይደለም። በዓለማችን ላይ እንደምናየው በሃይማኖት ማንነት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ በሚያራምዱ ኣገሮች ውስጥ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በሰፊው ከመስተዋላቸውም በላይ በኣንዳንድ ኣካባቢዎች ጽንፈኞችን እያፈራ እንደነ ኣልቃይዳ፣ ኣይ ኤስ ኣይ ኤስ (ISIS)፣ ኣልሽባብ፣ህዝቦላ፣ሃማስ የመሳሰሉትን ለዓለም ህዝብ ስጋት የሆኑ ድርጅቶችን ፈጥሮኣል። በዚህ በሃይማኖት ማንነት ላይ የሚመሰረትን ፖለቲካና በሃይማኖት ማንነት ላይ የሚገነባ ብሄራዊነትን በተመለከተ በዓለም ላይ ትኩረት ያገኘ ሲሆን በባህላዊ ማንነት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ ኣደገኛነቱ ብዙም ትኩረት ያገኘ ኣይመስልም። የማንነት ፖለቲካ ሃይማኖታዊም ይሁን በብሄር ላይ የተመሰረተ በዓለማችን የሁዋላ ታሪክ ውስጥ ጥሩ ምስክርነት የለው። የዓለምን የዘር ማጥፋት ታሪክ ብንመረምር በዓለም ላይ ከተፈጸሙት የዘር ማጥፋት ወንጀሎች መካከል ኣብዛኛዎቹ በኣንድም በሌላም መንገድ ወይ ሃይማኖታዊ ወይ ደግሞ ከብሄር ፖለቲካ ጋር በተያያዘ የመጣ ጥፋት ነው። በኣርመን፣ በሩዋንዳ፣ በናይጄሪያ፣ በቦስኒያ፣የተፈጸሙትን ወንጀሎች መጥቀስ ይቻላል። በጣም የታወቀው የሆልኮስት የዘር ማጥፋት ወንጀል መነሻም እነ ሂትለር ያመጡት ዘረኝነትን ሳይንሳዊ ለማድረግ በመሞከር (Scientific racism) ፖለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ስላደረጉ ነው። እነ ሂትለር ብሄራዊ ስሜትን ሊገነቡበት የፈለጉበት ፍልስፍና ኣደገኘ ነበር። የማንነት ፖለቲካ ብዙህ ለሆኑ ኣገሮች ቀርቶ ሆሞ ጂኒየስ ለሆኑ ኣገሮችም የሚጠቅም ኣይደለም። ሆሞ ጂኒየስ የሆኑ ኣገሮች ብሄራዊነትን ለመገንባት ብለው ባህላዊ ማንነታቸውን በጣም ካራገቡት ውጪያዊ ሶሺያል ካፒታላቸውን(External social capital) ይጎዳል።ብዙህነትን (Multiculturalism) ወይም ዓለማቀፋዊነት ላይ የሚኖራቸው ተሳትፎ ዝቅተኛ ከመሆኑም በላይ የዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብት እድገታቸውን ይገታዋል። ብሄራዊ ኩራትን(national pride) ኣገራቸው ለሰባዊና ለዴሞክራሲ እድገት በምታደርገው ጥረት፣ ለሳይንስና ቴክኖሎጂ እድገት ባላቸው ኣስተዋጾ፣ ዓለማቀፋዊ ተቋማትን ለማገዝ በሚያደርጉት ጥረት ዜጎች እንዲኮሩ ማድረግ በጣም ጥሩ ይመስላል። በቅርቡ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ስዊድን ፍርድ ቤት ሊከሰሱ እንደሆነ ስሰማ ሁለት ነገር ኣሰብኩ። ኣንደኛው ለውጥ ፈላጊው ኢትዮጵያዊ ምን ይሰማዋል? የሚል ነው። ይህንን ሳስብ ኣንደኛ ደስታ ሁለተኛ ሃዘን ነው። ደስታው የሚመነጨው የሚያዝንባቸውን መሪዎች ሊጠይቅ የሚችልበት ፍርድ ቤት ከባህር ማዶ መኖሩን ሲሰማ ሲሆን የሚያሳዝነው ደግሞ በሃገሩ ሰማይ ስር የራሱ ፍርድ ቤት ጉዳቱን ሳይፈርድለት በመቅረቱ ፍትህ ፍለጋ ባህር ማዶ በማለሙ ነው። በሌላ በኩል ያሰብኩት ኣሁን እኔ ስዊድናዊ ብሆን ይህን ዜና ስሰማ ምን ይሰማኛል? ብየ ነው። ስዊድናዊ ብሆን ኖሮ ደስ ይለኝ ነበር፣ በሃገሬ እኮራ ነበር። የምኮራውም በሃገራቸው ፍትህ ያጡ ህዝቦች እኔ በገነባሁት ነጻ ፍርድ ቤት ፍትህ በመፈለጋቸው ነው። ጥላ በመሆኔ የሌሎች ህዝቦች ፍትህ ማጣት ለእኔም እንደሚሰማኝ በማሳየቴ ደስታ ይሰማኛል እኮራለሁ ብየ ኣሰብኩ። ዜጎች በነጻ ተቋማት ላይ የተመሰረተ ብሄራዊ ኩራት እንዲያዳብሩ ማድረግ ጥሩ ይመስለኛል ለማለት ነው ይህን ያመጣሁት።

ኣገሮች ባህላዊ ማንነትን በኣንድ በኩል እየተንከባከቡ በሌላ በኩል ለመልቲ ካልቸራሊዝም ክፍት መሆን ካልቻሉ እየመጣች ያለችዋ ኣለም ታስቸግራቸዋለች። ብዙህ የሆኑ ኣገሮች ደግሞ ለየብቻ ሆሞ ጂኒየስ መሆን ፍትህ ሊያመጣ ይችላል የሚል እምነታቸው መሰረቱ ከዴሞክራሲ ጋር የማይሄድ መሆኑን መገንዘብ ካልቻሉ የብዙ ሰውን ህይወት እየጎዱ ሊኖሩ ይችላሉ።ስለ መልቲ ካልቸራሊዝም ሳስብ የሚሰማኝ ነገር ኣለ። ብዙ ጊዜ የምእራቡ ዓለም ባህል ተጫነን ሲባል እሰማለሁ። የምእራብ ዓለም ባህል ምን እንደሆነ በሚገባ ኣልገባኝም። የምእራብ ኣገራት ብዙ ናቸው። ስለ ባህል ካወራን እነዚህ ሃጋራት በጣም የተለያየ የየራሳቸው ባህል ያላቸው ናቸው። የምእራቡ ባህል ሲባል ምን ኣልባት የምእራብ ስልጣኔ ከሆነ ስልጣኔን መከላከል ኣስፈላጊ ዓይደለም።ስልጣኔ በራሱ መጥፎ ባህልን ኣይፈጥርም ነገር ግን ስልጣኔ ስናስገባ ወይም ስንፈጥር ማህበራዊ ለውጥ ውስጥ እንገባለንና በዚህ ለውጥ ጊዜ ለህብረተሰብ እድገት የማይጠቅሙ ክስተቶች ብቅ ብቅ ማለታቸው ኣይቀርም።ይሄ የማህበራዊ ለውጥ ኣንዱ ክስተት ነው። በዚህ ጊዜ እነዚህን ኣላስፈላጊ ክስተቶች ዳብረው ባህል ከመሆናቸው በፊት የመቅጨት ስራ በመንግስትና በህዝቡ በኩል መሰራት ኣለበት። ከዚህ ውጭ ስለ ምእራባዊያን መረዳት ያለብን ኣሁን ለምናያት የሰለጠነች ኣለም ያደረጉት ኣስተዋጾ እጅግ ከፍተኛ ነው። ለእኔ ከክርስቶስ በታች የዚህ ዓለም ብርሃን ናቸው። የምእራቡ ዓለም የስልጣኔ ባህል ዓለማችንን ከጎጂ ባህሎችና ልምዶች በማላቀቅ ላይ ይገኛል። ዓለም ስለ ሰብዓዊ መብት ያላትን ግንዛቤ እንድታሰፋ፣ ዴሞክራሲን እንድትለማመድ፣መልካም ኣስተዳደር እንዲሰፍን፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እዚህ እንዲደርስ የደከሙት ድካም ኣይዘነጋም። የዓለም ህዝቦች በሰብዓዊ መብት ዙሪያ እንዲነቁ፣ ገዢዎቻቸውን ስለ መብታቸው እንዲጠይቁ፣ ሰብዓዊ መብት የዓለም ህዝቦች ባህል እንዲሆን ከፍተኛ ኣስተዋጽዖ ኣድርገዋል። ታላላቅ የሰብዓዊ መብት ተሙዋጋች ድርጅቶችን በማቋቋም ታላቅ ኣስተዋጾ ኣድርገዋል። በኣፍሪካ በላቲን ኣሜሪካና በእስያ ኣገሮች የሚታዩትን ብዙ ጎጂ ልማዶች ለማስቀረት የወሰዱት እርምጃ ብዙ ለውጥን ኣምጥቱዋል። የምእራብ ኣገሮችና ኣሜሪካ ሌላው በዓለም ህዝቦች ዘንድ ሊረሳ የማይችለው ኣስተዋጾ ሴቶች መብታቸው እንዲከበር ማድረጋቸው ነው። ከባህል ጋር እየተያያዘ ሴቶች በብዙ ኣገራት ከፍተኛ በደል የሚፈጸምባቸው ሲሆን ይህንን ለማስቀረት የተጫወቱት ሚና በዓለም ሴቶች ዘንድ ተደናቂ ያደርጋቸዋል። ኣንድ ጊዜ ኣንድ ህንዳዊ ኣገኝቼ ስለ ህንድ ባህል ጠየኩት። የሰማሁት ነገር ስለነበረ ነው የጠየኩት። እንዴት ነው ሴቶችን በእሳት የማቃጠሉ ባህል እየጠፋ ነው ወይ? ብየ ጠየኩት። ኣዎ የሰባዊ መብት ተሙዋጋች ድርጅቶች እየለፉ ነው እየቀነሰ የመጣ ይመስለኛል ኣለኝ። ህንድ፣ ባንግላዴሽ፣ ፓኪስታን ኣካባቢ ሙሽራን ማቃጠል(bride burning) የሚባል ባህል ኣለ። በዚህ ባህል መሰረት ሴቲቱ ኣግብታ ባሉዋን ካላረካችና የምትሰጠው ጥሎሽ ህይወቱን ካልለወጠው በሚነድ እሳት ያቃጥላት ዘንድ የሚፈቅድ ባህል ኣለ። ይህንን የመሳሰሉ ጎጂና ኣስደንጋጭ ባህሎች ለማስቀረት የዓለምን ግማሽ የሚሆነውን ህዝብ ማለትም ሴቶችን ነጻ ለማውጣት ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ የሚታዩት የምእራብ ኣገሮች ህዝቦችና መንግስታት ናቸውና ሊመሰገኑ ይገባቸዋል።ከነሱ የምንማረው እጅግ ብዙ ነው። በኣፍሪካ ኣህጉራችን ውስጥ ብዙ ብሄሮች ሰውነታቸውን በስለት ሲዘለዝሉ ይታያል፣ ጠለፋ፣ ኣስገድዶ መድፈር፣ የሴት ልጅ ግርዛት፣ ስንቱ ተቆጥሮ። ደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ በነበርኩበት ጊዜ ስለ ሴት ልጅ የሰማሁት ኣስደንግጦኝ ነበር። በዚያ ብሄረሰብ ባህል መሰረት ሴት ልጅ የወር ኣበባዋ ሲመጣ ከቤት ትወጣና ጫካ ውስጥ ትደበቃለች። ለተውሰኑ ቀናት ብቻዋን ተገልላ ከቆየች በሁዋላ እንደገና ወደ ቤቱዋ ትመለሳለች።እንዲህ የመሳሰሉ ጎጂ ልማዶችን ለማስቀረት ህዝብን ማስተማር ስልጣኔን ማስረጽ ብቻ ሳይሆን የሚያስቀጣ መሆን ኣለበት። ከምስራቁ ዓለምም የምንማረው ኣለ። ሰራተኛነትን ከቻይናዊያንና ከኮርያዊያን እንማራለን። ማቴሪያል ካልቸራችንን ለማሻሻል ከኮርያና ከጃፓን የምናደርገው ግንኙነት በጣም ጠቃሚ ነው። በሌላ በኩል እኛ ኢትዮጵያዊያን በባህልም፣በታሪክም ብዙ የምናካፍለው ኣለንና ክፍት በመሆን ከዓለም ህዝቦች ጋር እውቀትን መከፋፈል ያስፈልጋል። በዓሁኑ ሰዓት ቴክኖሎጂ፣ ትራንስፖርት የሰው ልጅ እውቀት ዓለምን በጣም እያቀራረባት ስለሆነ የዓለም ህዝቦች እያዋጡ የጋራ ባህልን ሲመሰርቱ ነው እያየን ያለነው። ይሄ ደግሞ መልካም ነው። ዋናው ጉዳይ ኣንዳንድ ኣደገኛ የሆኑ ባህሎች ጎልተው ሲታዩ እነዚህን ባህሎች የራሳችንም ይሁኑ ማህበራዊ ለውጥን ተከትለው የመጡ ይሁኑ ቶሎ ብሎ የመቅጨት ስራ መስራት ነው።

የተነሳንበትን መሰረታዊ ጉዳይ እንዳንስት ወደ ፌደራሊዝሙ ጉዳይ እንመለስና የኢትዮጵያ ፌደራሊዝም ወይም የክልሎች መንግስታት ኣመሰራረት ብዙዎቻችን በብሄር ፌደራሊዝም እንግለጸው እንጂ እውነቱን ለመናገር ስም የለውም። የሶሲዮሎጂና የፖለቲካ ምሁራን ያልመከሩበት በነሲብ የተደረገ የክልልሎች መንግስታት ምስረታ የተካሄደ ነው የሚመስለው። ከሁሉም በላይ ትግራይን ለመከለል የተጨነቀውን ያህል ራሱ ፓለቲካው በሚያምነው “ራስን በራስ የማስተዳደር” መርህ ሌሎቹ ተከልለው ኣይታይም። ትግራይ ክልል ከተመሰረተ በሁዋላ ውሎ ኣድሮ እንዴውም ራያ ውስጥ ብዙ ትግርኛ ተናጋሪ ኣገኘን ብለው ወደ ትግራይ ከልለዋል ወልቃይትንም እንደዚሁ።ይህ ዓይነቱ ድርጊት የትግራይን ህዝብ ጠቅሞታል ለማለት ሳይሆን የመንግስትን ኣሰራር ለማሳየት ነው። በተለይ …በተለይ ….የደቡብ ህዝቦች ኣንድ ክልል የመሆኑ ነገር መነሻው ምን እንደሆነ ኣይታወቅም። እንደሚታወቀው ደቡብ ውስጥ ወደ 56 የሚጠጉ ብሄሮች ያሉ ሲሖን እነዚህን ብሄሮች በሙሉ ሰብስቦ ኣንድ ክልል ሊያደርጋቸው የሚችል ምን መመዘኛ ነበር ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል። ለምን የደቡብ ክልል ኣንድ ክልል ተባለ ኣይደለም ጥያቄው። ጥያቄው የደቡብ ክልል የሚባል ክልል ከተፈጠረ ለምን የሰሜን ክልል፣ የምስራቅ ክልል፣ የምእራብ ክልል እያለ ኣልቀጠለም የሚል ነው።ጥያቄው የህወሃትን መርህ ኣልባነት ለማሳየት ነው። በደቡብ ውስጥ ያሉ እነዚህ ብዙ ብሄሮች ኣንድ መንግስት ብቻ እንዲመሰርቱ የተደረጉበት ምክንያት ኣንዳንድ የወያኔ ሰዎች ሲናገሩ የደቡብ ብሄሮች በስነ ልቡና የተቀራረቡ እንደሆኑ ይገልጻሉ። ይሄ ምን ማለት እንደሆነ ኣይታወቅም። ለምሳሌ ያህል ጉራጌንና ኮንሶን ብንወስድ ሁለቱም ብሄሮች በቋንቋም ሆነ በባህል በጣም የተራራቁ ናቸው። ጉራጌ የሴም ቋንቋ ተናጋሪ ኮንሶ ደግሞ የኩሽ ቋንቋ ተናጋሪ ነው። በጉራጌና በኮንሶ መካከል ካለው የባህልና የቋንቋ ዝምድና ይልቅ የኣማራና የትግራይ የባህልና የቋንቋ ዝምድና ይቀራረባል። ይህንን የምለው ምን ያህል መርህ ኣልባ የሆነ ኣንድን ክልል ብቻ ለመጥቀም የተደረገ የክልል ኣመሰራረት እንደሆነ ለማሳየት እንጂ የኢትዮጵያዊያን ጥያቄ ይሄ ኣይደለም እንዴውም ባህልና ቋንቋ ኣንድ መንግስት መስርተን ለመኖር እንቅፋቶቻችን ኣይደሉም ከዚህ በፊት ለዘመናት ኖረናል እያሉ ነው።

የደቡብ ህዝብ በኣንድ መንግስት ስር ሲተዳደር “ራስን በራስ የማስተዳደር መብት” የሚባለው የኢህዓዴግ መርህ ትግራይ ላይ የሰራውን ያህል ኣይሰራም ማለት ነው። ክልል ኣመሰራረቱ በህዝብ ብዛት ነው እንዳይባል የትግራይ ክልል ከሲዳማ ህዝብ ጋር ተመጣጣኝ ነበር። ለዚህ ነው የሲዳማ ህዝብ እኛስ ለምንድነው በዞን ደረጃ የምንታየው ለምን መንግስት ኣንሆንም ብለው እየጠየቁ ያሉት። መንግስት ራሱ ባወጣው መስፈርት መሰረት ነው እየጠየቁ ያሉት። ያም ሆኖ ግን ትግራይ ላይ የሰራው “ራስን በራስ የማስተዳደር” መብት ሲዳማ ላይ ኣይሰራም። በመሰረቱ የብሄርን ፖለቲካ ተከትሎ የመጣው የፌደራል ኣወቃቀሩ ዝም ብሎ የተዋገረ ስለሆነ ጥርት ያለ ምላሽ ኣይገኝበትም። የደቡብ ህዝብ ደስ የሚለው ወያኔ ያንን ኣለ ያንን ብዙም ከቁብ ሳይቆጥር ኣንድነቱን ጠብቆ ይኖራል። ጥያቄው ግን የመርህ ጥያቄ ነው። የደቡብ ህዝብ ኢህዓዴግ ከገባ በሁዋላ የፖለቲካ ተሳትፎው ጥያቄ ለማኝ ነበር። እንደሚታወቀው ይህንን የብሄር ፖለቲካ ተከትሎ ኢህዓዴግ እንደገባ ሁሉም የደቡብ ብሄሮች የፖለቲካ ድርጅት ኣቋቁመው ነበር። እነዚህ የየብሄሩ የፖለቲካ ድርጅቶጅ ቁጥራችሁ ትንሽ ስለሆነ ለመንግስትነት ኣትበቁም ኣይነት ተባሉና የደቡብ ህዝቦች የሚባል መንግስት ሲመሰርቱ ደህዴግ የሚባል የክልል ፓርቲ ተጠናክሮ ወጣ ተባለ። ይህ ድርጅት በነዚያ ከየብሄሩ በመጡ ፓርቲዎች የተዋቀረ ግንባር ነው። የሚገርመው ይህ ግንባር ወደ ፌደራል ሲመጣ እንደገና ኢህዓዴግ ከተባለው ኣስገራሚ ድርጅት ጋር ሌላ ግንባር ይፈጥራል ይህ ማለት እነዚያ በየብሄሩ የተመሰረቱት ድርጅቶች የኢህዓዴግ የልጅ ልጆች ይሆናሉ ማለት ነው። ወይም ኢህዓዴግ ኣያት ነው ማለት ነው። ኢህዓዴግ ለህወሃት ኣባት እንደሆነው ሁሉ ለነዚያ ለደቡብ ብሄሮች ድርጅቶች ኣባት መሆን ኣልቻለም ማለት ነው። በቁጥራቸው ምክንያት የልጅ ልጅ ሆነው ሲኖሩ ሲኖሩ ቆዩና ከብዙ ኣመታት በሁዋላ በኣስራ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ኣምስት የየብሄሩን ፓርቲ እያፈረሱ ያን ደህዴግ የተሰኘውን ኣንድ ክልላዊ ፓርቲ ኣድርገው እነሱ ከሰሙ። ይህ የሚሻል ቢሆንም ኣሁንም ግን ከመንግስት ኣጠቃላይ የፖለቲካ ኣወቃቀር ጋር ሲታይ የደቡብ የፖለቲካ ተሳትፎ ጉዳይ ጥያቄ ያለበት ነው። የሎጂክ ጥያቄዎችን የሚለምን ሁኔታ የከበበው ነው። የኣሁኑን ጠቅላይ ሚንስትር ኣቶ ሃይለማርያምን ከብሄራቸው ኣንጻር ራሳቸውን የሚገልጹበት የፖለቲካ ድርጅት የላቸውም ማለት ነው። እንደ ህወሃት፣ ብዓዴን፣ ኦህዴድ ጓዶቻቸው ራሳቸውን ፖለቲካዊ በሆነ መንገድ የሚገልጹበት ድርጅት ሳይሆን ያላቸው ከመልክዓ ምድር ኣንጻር የሚገልጹበትን ድርጅት ነው የሚመሩት። ደቡብ ቢሄዱ ደግሞ የመጡበት ብሄር የፖለቲካ ድርጅት ባይኖራቸውም ኣጠቃላይ የፖለቲካው ስሜት የሚገፋቸው ሰዎች የወላይታ ተወካይ ነው የሚያደርጓቸው። ጨዋታው በየቤትህ እደር ከሆነ እንዲህ ዓይነት ብዙ መልስ የሌላቸው ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ፌደራሊዝም ነው ያለው ኣገራችን ውስጥ።

የኢትዮጵያ የፌደራሊዝም ጉዳይ ሰሜኑን በቋንቋ ደቡቡን በጂኦግራፊ የሸነሸነ ሲሆን የክልል መንግስት ኣመሰራረቱ የኢህዓዴግን መርህ ኣልባነት ምህንድስናው ኣንድ ኣካባቢን ብቻ እንዳሰቡት ለማድረግ የተሰራ እንጂ ወጥነት የሌለው ነው። ዋናው የኢትዮጵያ መንግስት መገለጫ በብሄር ፖለቲካ ሲሆን ቡድኖች በባህላዊ ማንነታቸው ራሳቸውን ፖለቲካዊ በሆነ መንገድ እንዲገልጹ የሚያደርግ ሲሆን የደቡብ ብሄሮች ግን ራሳቸውን ከፖለቲካ ኣንጻር የሚገልጹት በብሄር ማንነታቸው ሳይሆን በጂኦግራፊ በመገናኘታቸው ነው። ከፍ ሲል እንዳልኩት ኮንሶ ከጉራጌ ይልቅ በባህልም በሃይማኖትም ለኦሮሞ ነው የሚቀርበው። የኮንሶ ህዝብ ዋቃ የተሰኘ ኣምላክ የሚያመልክ ሲሆን ከኦሮሞ ጋር የተወራረሰ ነው። በቡርጂና በሱርና ብሄረሰብ መካከል ካለው የባህልና የቋንቋ ግንኙንነት ይልቅ ቡርጂዎች ለጉጂ ኦሮሞዎች የቀረበ ነገር ኣላቸው። ብዙዎቹ የቡርጂ ማህበረሰብ ኣባላት ኦሮምኛ ተናጋሪዎች ናቸው። ደቡብ ውስጥ የሴም፣ የኩሽ፣ የኦሞና የናይሎ ሳሃራ ቋንቋ ተናጋሪዎች ያሉበት የኢትዮጵያ ተምሳሊት የሆነ ክልል ነው።

እንግዲህ ደቡብ ኢትዮጵያዊያን ከዚህ ከሃገሪቱ የምንነት ፖለቲካ (Identity politics) ኣንጻር ራሳቸውን የሚገልጹት ከደቡብ ኣንጻር ነው ማለት ነው። እንዴው ወያኔ ራሱ የሚለውን ተከትለን በራሱ ሎጂክ እንጠይቀው ብለን እንጂ የብሄር ፖለቲካው ምን ሊጠቅማቸው።
ለስራ ጉዳይ ለተወሰነ ጊዜ ደቡብ ኣካባቢ ነበርኩና የታዘብኩት ነገር የመገንጠል ጥያቄ ሲነሳ ለደቡብ ህዝቦች የሚመች ጥያቄ ኣይደልም። ሌሎች ብሄሮች ሰሜን ምስራቅ ምእራብ ሳይባሉ እነሱን በጂኦግራፊ ብቻ ደቡብ ብሎ መሰየሙ ግራ እንደሚያጋባቸው ተረድቻለሁ። ያም ሆኖ ግን የኢትዮጵያን ኣንድነት ስለሚናፍቁ ኣንድ ቀን የዚህ የብሄር ፖለቲካ ሲቀር ጥያቄያቸው እንደሚፈታ ያስባሉ።

በኣጠቃላይ በብሄር ላይ የቆመ ፖለቲካ የምታራምድ ኣገር፣ ራስን በራስ ማስተዳደር ከዳቦና ከእንጀራ በላይ ሆኖ ኣግኝቸዋለሁ ለሚለው መንግስት ኣንዳንዶቹን ብሄሮች መስፈርቱ ባልታወቀ መልኩ ለመንግስትነት ማእረግ ኣትበቁም ወይ በልዩ ወረዳ ወይ በዞን ደረጃ ተሰየሙ መባሉ ኢፍትሃዊ እኮ ነው። ቡድንን ቡድን የሚያሰኘው የህዝቡ ብዛት ሳይሆን ቋንቋውና ባህሉ ሲሆን የማንም ቋንቋ ከማንም ኣይበልጥም ኣያንስምና እነዚህ ቡድኖች ሁሉ የክልል መንግስትነት ጥያቄ ቢያነሱ ምን ጥፋት ኣላቸው?

ሰማኒያ የሚሆኑ ቡድኖች ባሉበት ኣገር ቁጥራቸው ኣነስ ያለውን “ኣናሳ” እያሉ ወደ ኣንዱ ለጠፍ እያደረጉ ዘጠኝ ክልል መስራት ምን ይባላል? ፍትህ የጎደለው እንዲሆን ያደረገው ራሱ መንግስት ይዞት የተነሳው እምነት ነው። ኣድካሚ የሆነ እምነት:: የኢትዮጵያን የቡድንም ሆነ የግለሰብ ጥያቄ የማይመልስ እምነት። በጣም ያሳዝናል።

በኣጠቃላይ የኢትዮጵያ ክልል ኣመሰራረት ከራሱ ከኢህኣዴግ ፖለቲካ ጋር የተጋጨ፣ ከሁሉም በላይ ከኢትዩጵያ ተፈጥሮ ጋር የተጋጨ፣ ሳይንሳዊ ያልሆነና መርህ የጎደለው በመሆኑ ይህ ነገር የሚመጣ መንግስት ሲመጣ በተሻለ ክልል ማሰዳደር ይቻል ዘንድ ኢትዮጵያዊያን ከወዲሁ ልናስብበት ይገባል።
በኣጠቃላይ ይህን ሁሉ የማወራው የኣቶ መለስ ምህንድስና ምን ያህል እንዳሻው የተዋቀረ እንደሆነ ለመግለጽ ነው። ከዚህ በላይ የኢትዮጵያን የኣርባ ኣመት የማንነት ጥያቄ በተሻለ የሚመልስና ወጥነት ያለውና በመርህ ላይ የተመሰረት ፌደራሊዝም ስርዓት ለመመስረት ጥቂት ኣሳብ ለማቀበል እፈልጋለሁ።
የኣዲሲቱ ኢትዮጵያ የፌደራል ስርዓት እንዲህ ቢሆንስ?

በዚህ በወያኔ ብሄርተኛ ኣስተዳደር የተቆጣን ሰዎች ለለውጥ ስንታገል የምንፈልጋት ኢትዮጵያ ምን ዓይነት እንደሆነች በሚገባ ስለን ማሳየት ኣለብን።ምን ዓይነት የፌደራል ስርዓት ነው የምንፈልገው። ያለፈውን የኣርባ ኣመት ጥያቄ እንዴት ነው የምንፈታው ብለን ቀድመን ጥንቅቅ ኣድርገን ልናስብበት ይገባል።የወደፊቱዋን የፈለግናትን ኢትዮጵያን በጸዳ ሁኔታ ኣሰተዳደራዊ ቅርጹዋን ማሳየት ይጠበቃል። ኣንዳንድ ሰዎች የኣሁነ ዘመን ትግላችን ከፍትህና ከዴሞክራሲ ጥያቄም በላይ ሃገርን የማዳን ስራ ተደርጎ ሊወሰድ ይገባዋል ይላሉ። ይህን ጉዳይ የምጋራው ሆኖ ኣገርን የሚያድን ጥርት ያለ ኣማራጭ የፖለቲካ ስርዓት ለኢትዮጵያ ህዝብ ማሳየት ይጠበቃል። በዚህ ረገድ ባለፈው ጊዜ ደጋግሜ በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ካልኩት ኣሳብ የሚቀዳ ኣንድ የመንግስት ኣወቃቀር ጠቆም ለማድረግ ነው ፍላጎቴ።
የክልል ኣመሰራረቱ የሚመነጨው ኢትዮጵያን ከምናይበት እይታ ነው። በዚህ ኣገባብ ኢትዮጵያን የምናየው በስምምነት ላይ ከተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ኣሳብ ኣንጻር ነው።ከሁሉ የሚቀድመው በብሄራዊ እርቅ መንገድም ይሁን በሽግግር መንግስት ስም ቡድኖችን የሚያወያይ ከፍተኛ ኣገራዊ ኣጀንዳ ይዞ ወደ ስምምነት መምጣት ነው። ለውይይት ከምናቀርበው ኣሳብ ውስጥ ኢትዮጵያን በተሻለ ሊያስተዳድር የሚችል ጥበብ ማሳየት ከቻልን ቡድኖች የማይስማሙበት ጉዳይ የለም። ይህ ወይይትና ስምምነት የፓርቲዎች ጉዳይ ኣይደለም። ባለፉት ኣርባ ኣመታት ህዝባዊ ውክልና የሌላቸው ፓርቲዎች ልክ ህዝብ የመረጣቸው ይመስል ኣንዴ የማንነት ፖለቲካ ይሻላል፣ ኣንዴ ሶሻሊዝም ኣንዴ ምን እያሉ ቆይተዋል። ይህ ጉዳይ ተለውጦ ኣሁን ኣንድ ኢትዮጵያን ኣጠናክሮ ሊገነባ የሚችል የስምምነት ኣሳብ ይዞ ቡድኖችን በቀጥታ ማነጋገር ያስፈልጋል። ህዝቡ በቀጥታ ተሳታፊ የሆነበት ከፍተኛ ውይይት ተደርጎ ኣንድ ኪዳን ሊፈርም ያስፈልጋል። ከዚያ በሁዋላ ፓርቲዎች እየተነሱ ህገ መንግስት ኣርቅቀው እያስጸደቁ መንግስት እየተቀያየረ መኖር ይቻላል። ኢትዮጵያዊያን ልንወያይበት ከሚገባው ጉዳይ መካከል ኣንዱ የዚህ የፌደራሊዝም ጉዳይ በመሆኑ ፌደራሊዝሙ ብዙ የሆነችውን ኢትዮጵያን ባህላዊና ፖለቲካዊ ማንነቱዋን ለይቶ የሚያስተዳደር ቅርጽ ሊይዝ ይገባዋል። በዚህ መሰረት በሁለት ፌደሬሽን የምትመራ ሁለት መንግስታት ያሉዋት ኣገር ኣድርገን ብንሰራት የተሻ ይሆናል። ይህ ሁለት መንግስት ማለት ኣንደኛው ባህላዊ መንግስት ሲሆን ይህ መንግስት በህገ መንግስት ሃላፊነት የተሰጠው ባህላዊ ጉዳዮችን ለይቶ የሚንከባከብ ሲሆን ሌላው መንግስት ደግሞ ፖለቲካዊ ጉዳዮችን የሚመራ ነው። እነዚህ ሁለት መንግስታት ቢመሰረቱ ኣንደኛ የማንነት ፖለቲካ ጥያቄያችንን ያቃልላል። ሁለተኛ ብዙህነታችንን ኣደባባይ ኣውጥቶ መልካችንን ያሳያል። ከዚህም በላይ ሰላምና ልማትን ለማፋጠን የማትከፋፈል ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማሳለፍ ይረዳናል።

ኢትዮጵያ ኣንድ ናት ስንልም ከነዚህ ከሁለት ዋልታና ማገር የተሰራች መሆኑዋን እያሰብን ነው። በመሆኑም ኢትዮጵያ ሁለቱንም ማንነቶቹዋን ሳያደባልቅ የሚያስተዳድር ፌደራሊዝም ልትመሰርትና በሁለት መንግስታት ልትተዳደር ትችላለች። እነዚህ ሁለት መንግስታት ኣንዱ የባህል መንግስት ሲሆን ሁለተኛው ፓለቲካዊና ዴሞክራሲያዊ የሆነ መንግስት ነው። ሁለቱም መንግስታት በመሰረታዊ ህግ በሚገባ የተለየ ስልጣንና ተግባር ኖሩዋቸው ይኖራሉ። ፖለቲካዊው መንግስት ዳይናሚክ ሲሆን በየጊዜው ዴሞክራሲን እያሳደገ ዘመናዊ ኣሰራርን እያዳበረ ኣገሪቱን ወደተሻለ ህይወት ይመራል። ባህላዊው መንግስትም ባህሎቻችንን እየጠበቀ በመሰረታዊ ህጉ ላይ ያለውን ሃላፊነት እየተወጣ ይኖራል። ባህላዊ መንግስትን ስንመሰርት ዘመናዊነት መጣ ብለን ጥለን የነበርነውን ጠቃሚ ባህል ሁሉ እንድናነሳ ያደርገናል። የየቡድኖች ነገስታት ወደ ኣደባባይ በማውጣት በምንመሰርተው ህብረ ብሄር ቤተ መንግስት ይመጡና ከፍ ብለው ይታያሉ። ኮሚንዝም ያስጣለንን ባህል ሪስቶር እያደረግን ታሪካዊ ሃገራችንን የቀድሞ የፈጠራ ውጤቶቹዋን ኣክብረን ካዲሱ ትውልድ ፈጠራ ጋር ጎን ሎጎን ማስኬድ እንችላለን። ለኣርባ ኣመት የቆየውን የማንነት ጥያቄ በማቃለል ፣ ማንነትን ሳናወዳዽር የምንፈጥረው ስርዓት የረጋና ሰላም የሰፈነበት ይሆናል። በተለይ እኛ ኢትዮጵያዊያን ከኛ ሁኔታና የህይወት ልምድ፣ ካለፍንበት ረጅም ጎዳና ኣንጻር ፖለቲካዊና ባህላዊ ማንነቶችን ማደባለቅም ሆነ ኣንዱን ከኣንዱ የማበላለጡ ስሜት ጎድቶን ኣጨቃጭቆን ይታያልና ውድ ድር ውስጥ ሳናስገባ ባለንበት ቡድን ስም ራሳችንን ብንገልጽ ክፋት የለውም። ኣንድ ዜጋ ክርስቲያን ነኝ ብሎ ራሱን በዚህ ሃይማኖታዊ ማንነት ሲገልጽ ከኢትዮጵያዊነትህና ከክርስትናህ የቱን ታስቀድማለህ ወይም የቱ ይበልጣል እያሉ መፈተን ጠቀሜታ የለውም። ባህላዊ ማንነቶቻንንም እንደዚያ ማየት ነው። ኣንድ ዜጋ በባህላዊ ማንነትም ሆነ በፖለቲካዊ ማንነቱ ራሱን የሚገልጽበት ሁኔታ መኖር ኣለበት። በዚህ ጉዳይ ላይ ከዚህ በፊት ብዙ ብያለሁና ይብቃ። ይህንን ማንነቶቻችንን መለያየታችንን የሚያሳየው የሁለቱ መንግስታት ምስረታችን ነው። የምንመሰርታቸው መንግስታት ሌሎች ኣካባቢዎች ባህላዊ ኣስተዳደር ኣለ እንደሚባለው ሳይሆን በሚገባ በመሰረታዊ ህጉ የስልጣን ክፍፍል ያደረገ ቤተመንግስት የመሰረቱ መንግስታት ናቸው የሚኖሩን። ከህገ መንግስት ወይም መሰረታዊ ህጉ በላይ በሚውለው ኣዲስ ኪዳን ስር የሚመሩን ሁለት መንግስታት ማበጀታችን ኣንድ የመጀመሪያ ርምጃ ይሆንና ከዚህ በሁዋላ የክልሎችን ኣመሰራረት ወይም የፌደራሉን ኣወቃቀር በተመለከተም ሁለቱም መንግስታት የየራሳቸው ኣስተዳደራዊ ክልል ይኖራቸዋል። የፖለቲካው መንግስት ክልሎችን ሲገናባ ኣስተዳደራዊ ኣመቺነትን እያየ የሚከፋፍል ሲሆን በመሬት ላይ የሚነበብ ክልል ይኖረዋል። ስልጣንና ፍትህ ወደ ህዝቡ በተቻለ መጠን የሚቀርብበትን ክልሎች ማቆም የፖለቲካው መንግስት ስራ ነው። ፌደራሊዝም ለትላልቅ ሃገራት ተመራጭ ይሁን እንጅ ውድነት(expensiveness) ስላለው ይህንንም ከግንዛቤ ያስገባ ፌደራሊዝም ያስፈልጋል። ኢትዮጵያ ካላት የቆዳ ስፋት ኣንጻር ከኣራት የማይበልጥ ስቴቶች ቢኖሩዋትና ኣራቱም ሰሜን፣ደቡብ፣ ምስራቅና ምእራብ ኢትዮጵያ ተብለው ቢሰየሙ ጥሩ ሊሆን ይችላል። ስልጣንን ከስቴት መንግስታት ቀጥለው የሚፈጠሩ የመንግስት ሃየር ኣርኪዎች ማውረድ ኣስፈላጊ ነው።

ሌላው መንግስት ማለትም ባህላዊ መንግስት ያልነው ደግሞ በመሬት ላይ የሚነበብ ክልል ወይም ስቴት ኣይኖረውም። የኣንድ ባህላዊ በድን ኣባላት በመላው ሃገሪቱ ተሰራጭተው የሚኖሩ ከሆነ እነዚህ ኣባላት በያሉበት ባህላቸውን የሚጠብቁበት የሚንከባከቡበት ሁኔታ ነው የሚኖረው። የኦሮሞ ስቴት፣ የኣማራ ስቴት፣ የሙርሲ ስቴት ወዘተ ስንል ባህሉና ቋንቋው ነው ሊታየን የሚገባው። እነዚህ ስቴቶች ኣሳባዊ ይሆኑና ኣባላት በያሉበት የዚያ ኣሳባዊ ስቴት ኣባል ይሆናሉ የሚጠበቅባቸውንም ያደርጋሉ። ኣንዳንድ ጊዜ ባህላዊ መንግስቱ ኣስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው የመንግስትን መዋቅር ሊጠቀምበት ይችል ይሆናል።
ይህ ባህላዊ መንግስት ባለፈው ግዜ እንዳነሳነው የኣርበኞች ቤት የሚባል ካውንስል የሚያቋቁም ሲሆን ይህ ቤት የሚመሰረተው በቡድኖች ነገስታት ይሆናል። ከዚያ ስር የሚያዋቅራቸው 3 ቤቶች ይኖሩታል። ኣንደኛው የባህልና ቋንቋ ጠባቂና ተንከባካቢ ቤት፣ ሁለተኛው የኬር ቴከር ቤት፣ ሶስተኛው የሰላምና የእርቅ ግጭት ኣስወጋጅ ቤት ይሆናሉ። በባህልና ቋንቋ ጥበቃ ስር ተጨባጭና ተጨባጭ ያልሆኑ ባህሎችን የሚንከባከብ ክፍልና የብሄራዊ ሙዚየም ይኖረዋል።በኣጠቃላይ የባህላዊው መንግስት የራሱ የሆነ ሲስተም ሲኖረው ፖለቲካውም እንዲሁ በፊናው የራሱን ሲስተም ዘርግቶ በየተወሰነ ጊዜው ምርጫዎችን እያደረገ ይኖራል።

በዚህ ኣርቲክል ውስጥ በነዚህ ንኡስ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ትንታኔ ኣንሰጥም። ዋናው ኣላማ ኣጠቃላይ መዋቅሩን ማሳየት ሲሆን በዚህ ዓይነት ኣወቃቀር ሰላምን፣ ፍትህን ለማሳለጥ በኢትዮጵያ ይመረጣል ለማለት ነው። ኣጠቃላይ ቅርጹ በሚከተለው ቻርት የተገለጸ ነው።
የCCU የመንግስት ኣወቃቀር
ኣንዳንድ ፓርቲዎች ይህ ኣንገብጋቢ ጉዳይ ኣይደለም ወያኔን መጣል ነው ኣንገብጋቢው ጉዳይ የሚሉ ከሆነ ትክክል ኣይመስለኝም። የሆነ የጠራ ኣማራጭ በኣንድ እጃችን ይዘን ነው ለለውጥ መታገል ያለብን ብየ ኣምናለሁ። በመሆኑም ኣንዳንድ የፖለቲካ ድርጅቶች ሊለውጡዋት ያሰቡዋትን ኢትዮጵያ እንዲህ የሚያዩዋት ከሆነ ፕሮግራማቸው ውስጥ ኣስገብተው ለህዝብ ቢያስተዋውቁ ጥሩ ነበር።

ለማናቸውም እግዚኣብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!
ኣስተያየት ካለ እነሆ ኣድራሻየ
geletawzeleke@gmail.com


የኮብላዩ ሚኒስትር ወጎች –ከተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)

$
0
0

በዚህ ተጠየቅ ጨርፈን የምንመለከተው በኮሙኑዮኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ የነበረውና ዛሬ በስደት የሚገኘው የአቶ ኤርሚያስ ለገሰን “የመለስ ትሩፋቶች፣ ባለቤት አልባ ከተማ” የተሰኘው መጽሐፍን ነው፡፡ የመድብሉ ጻሐፊ ኤርሚያስን በግል አላውቀውም፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአካል ያየሁት አቶ በረከት ስምዖን እርሱን እና ሽመልስ ከማልን ምክትሎቹ አድርጐ በሚኒስቴር ዲኤታ ማዕረግ መሾሙን በግዮን ሆቴል ለጋዜጠኞች ይፋ ባደረገበት ዝግጅት ላይ ነው፡፡ ከዚህ ለጥቆ፣ በኢትዮጵያ የቀድሞው የአሜሪካ አምባሳደር ዶናልድ ቡዝ በኤምባሲው ግቢ በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው ባዘጋጁት የዕራት ግብዣ ላይ (ግንቦት 19/2001 ዓ.ም) ድንገት ተገናኝተን እጅ ለእጅ ተጨባብጠን ሰላምታ ተለዋውጠናል፤ ለመጨረሻ ጊዜ የተያየነው፣ በኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ግንቦት 7 እና እነጀነራል ተፈራ ማሞን በተመለከተ መግለጫ በተሰጠበት ዕለት እንደ አፄ ኃይለሥላሴ የክብር ዘብ፣ ከሽመልስ ከማል ጋር በረከት ስምዖንን ግራና ቀኝ አጅቦ በተገኘበት ወቅት ነው፡፡ በተቀረ በመንግስት ሥልጣን ሲገለጥ ብዙም አላስተዋልኩም፡፡ ከዚህ ይልቅም ኢህአዴግነቱን ለማሳየት የሞከረበትን አንድ ገጠመኝ አስታውሳለሁ፤ ይኸውም “የፍትሕ” ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ የነበረው እና አሁን በስደት ሀገር የሚገኘው ባልደረባዬ ማስተዋል ብርሃኑን ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ባለው ቢሮው ድረስ በመጥራት ከባድ ዛቻና ማስፈራሪያ ከሰነዘረበት በኋላ፣ ዛሬ የቀድሞ ጓዶቹ ሥራዬ ብለው እንደቀጠሉበት አይነት በጋዜጣው ላይ የሀሰት ውንጀላ ደርድሮ ሲያበቃ፣ ከኃላፊነቱ ራሱን እንዲያገል አስጠንቅቆት እንደነበር ከራሱ ከባልደረባዬ ማስተዋል አንደበት ሰምቻለሁ፡፡
temesgen-desalegn
የሆነው ሆኖ አቶ ኤርሚያስ ከላይ በተጠቀሰው መጽሐፉ በተመላኪው ሰው አመራር “ሁሉን አዋቂነት” ላይ የቆመው መንግስት ምን ያህል በጠባብ የወንዝ ልጅነት የተተበተበ እና በዘራፊ ባለሥልጣናት የተዋቀረ እንደሆነ በስፋት ተርኮልናል፡፡ በተለይም ሙስና እና የህወሓት ካድሬዎች የበላይነትን በተመለከተ በማስረጃ አስደግፎ በተዋበ ስነ-ጽሑፋዊ ቋንቋ ዘርዝሮልናል (በርግጥ “የጋዜጠኛው” አሊያም “የደራሲው ማስታወሻ” የሚያነቡ እስኪመስልዎ ድረስ የመጽሐፉን አርትኦት ተስፋዬ ገ/አብ ወይም የተስፋዬ ብዕር ተፅእኖ ያለበት ደራሲ ብዙ እንደለፋበት በግልፅ ማስታወቁን መካድ አይቻልም)፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎንም ዛሬም ከአገዛዙ ጋር የተሰለፉ የቀድሞ ጓዶቹ ለህሊናቸው ሲሉ በድብቅ የሚፈፀሙ ሕገ-ወጥ ድርጊቶችን ደፍረው እንዲያጋልጡ በጠየቀበት ብዕሩ፣ የራሱንም ጥፋቶች እና በትዕዛዝም ይሁን በግል ተነሳሽነት በደል ያደረሰባቸውን ንፁሃን በይፋ ይቅርታ ቢጠይቅ መልካም ነበር፤ አሁንም ቢሆን ለዚህ አይነቱ ቅንነትና በጎ አርአያነት ገና አልረፈደም፡፡ ርግጥ ነው የስደት ምርጫው ባደረጋት ሀገረ-አሜሪካ ባሳተመው መጽሐፉ ውስጥ ድርጅቱ ኢህአዴግ ይሰራው በነበረው ሕገ-ወጥ ድርጊትና የጭካኔ እርምጃ አልፎ አልፎ ቢሮውን ዘግቶ እንደሚያለቅስ፣ ባስ ሲልም ህሊናውን ቆጥቁጦት ታምሞ አልጋ ላይ እንደሚውል በመግለፅ የራሱን ጲላጦሳዊነት ለመስበክ መልፋቱን ስናስተውል፤ ጸሐፊው የሥርዓቱ ጋሻ-ጃግሪ በነበረበት ወቅት የበደለውን ሕዝብ ይቅርታ የመጠየቅ ዝግጁነትም ሆነ ፍላጎት (ቢያንስ በዚህ ሰዓት) የለውም ብለን ማዘናችን አይቀርም፡፡

እንዲሁም ከሀገር እንዲወጣ የተገደደበት ምክንያት ተብሎ ስለተናፈሰው ወሬ ትንፍሽ አለማለቱ በበኩሌ አስተዛዛቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፤ በወቅቱ የስደቱ መነሾ ተደርጎ በከተማዋ በስፋት የተናኘው፣ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖቹ እና “የግንቦት 7 አባላት ናችሁ” የተባሉ ግለሰቦች ለእስር መዳረጋቸውን ተከትሎ ለአንድ ዓለም አቀፍ ሚዲያ “ሙከራው መፈንቅለ መንግስት ነው” የሚል መግለጫ በመስጠቱ እንደነበረ ነው፤ በዚህም እጅግ የተበሳጨው ጠ/ሚኒስትሩ፣ አለቃው በረከት ስምዖን ላይ ጭምር የጭቃ-ጅራፉን ከማወናጨፉም በላይ፣ ኤርሚያስን ያለ ሥራ እንዳንሳፈፈው መወራቱን አስታውሳለሁ፤ ይህንን መረጃ አምኖ ወደመቀበሉ የሚገፋን ደግሞ በዚያው ሰሞን መለስ ዜናዊ ራሱ በቴሌቪዥን ቀርቦ ‘…የተደረገው ነገር እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፣ ከአልቃይዳና አልሸባብ ጋር ሲነፃፀሩ የእኛዎቹ አማተሪሽ (ልምድ አልባ) ናቸው’ እያለ የሚኒስትር ዴኤታውን ንግግር ለማስተባበል ሲዳክር የመስተዋሉ እውነታ
ነው፡፡ እርሱም ቢሆን ከዚህ ግልፅ ሹክሹክታ በኋላ በትምህርት ሰበብ ሀገር ለቅቆ መሰደዱ የአንድ ሰሞን የከተማ ወሬ ሆኖ ነበር፡፡ እነሆም ወንድም ኤርሚያስ ለገሰ ይህንን ጉዳይ ዳጉስ ባለው መጽሐፉ ውስጥ ሽራፊ ገፅ ሊሰጠው አለመቻሉ እዚህ ጋ በትዝብት እንዳነሳው መገደዴን በትህትና እገልፃለሁ፡፡ አሸንፈሀልና በዝብዘህ ብላ!

ህወሓት-ኢህአዴግ ወደ ሥልጣን ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ፣ በግርማ ብሩ አነጋገር “ደሀ-ዘመም” (በመጽሐፉ የተጠቀሰ) እንደሆነ ለማሳመን የሚሞክርበት ብልጠት፣ ራሱን ለሙስና ፅዩፍ አስመስሎ በማቅረብ ነው፤ ይህን አይነቱን ስሁት አመለካከት በሕዝብ ውስጥ ለማስረፅ ጥቂት የፖለቲካ መታመን-ጉድለት ጥርስ ያስነከሰባቸውን ጉምቱ ጓዶቹን “ሙሰኛ” በሚል ወንጅሎ በወህኒ የቃየል መስዋዕት ሲያደርጋቸው ተስተውሏል፤ እርምጃውንም በፓርላማው መድረክ ሳይቀር ሲኩራራበትና ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ሲያውለው ተመልክተናል (ከሩቁ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ታምራት ላይኔ እና መከላከያ ሚኒስትሩ ስዬ አብርሃ፤ ከቅርቡ ደግሞ የገቢዎችና ጉምሩክ ዳይሬክተር መላኩ ፈንቴ፣ የደህንነት ኃላፊው ወ/ስላሴ እና መሰል ባለሥልጣናትን እስር ልብ ይሏል)፡፡ የሚኒስትር ዴኤታው መጽሐፍ፣ መለስ እና ጓዶቹ ካደነቆሩን በግልባጩ ‘የዘረፋ መሪዎች’ የሚላቸው ሁለት የህወሓት ሰዎች፣ በባላንጣነት ተሰልፈው እንዴት የሀገር ሀብት ለመቀራመት ይሽቀዳደሙ እንደነበር አጋልጧል፤ አዜብ መስፍንን እና አርከበ እቁባይን፡፡

“እነ አርከበ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ ከመምጣታቸው ጥቂት ወራት በፊት በህወሓት ውስጥ መደናገጥ ተፈጥሮ ነበር፡፡ የህወሓት ዳግም መከፋፈል ምክንያት ደግሞ በወ/ሮ አዜብ እና አርከብ ቡድኖች መካከል አለመግባባቶች መፈጠራቸው ነበር፡፡ መነሻው መረን የለቀቀ የጥቅም ግጭት ሲሆን ዓላማው የህወሓት ኢንዶመንቶችን መቆጣጠር ታሳቢ ያደረገ ነበር፡፡” (ገፅ 25) ከዕለት ተዕለትም ይህ ሁኔታ የተካረረ ልዩነት ፈጥሮ፣ ፖለቲካዊ ቁመና በመላበሱ፤ አርከበ እቁባይ፣ ህወሓት መገፋቱን እና መለስ በበረከት በኩል የድርጅቱን ካድሬዎች እያስጠቃ ነው የሚል ክስ ከማጎኑም ባሻገር፤ ወደኋላ ተጉዞ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት የተጠናቀቀበትን መዛግብት አቧራ በማራገፍ፣ ተጠያቂነቱን ከፍ ሲል ወደ መለስ ዜናዊ፣ ዝቅ ሲል ደግሞ ወደ በረከት ስምዖን በመወርወር ማጠቋቆሩ ያመጣውን ውጤት እንዲህ ሲል ገልፆታል፡- “በሂደት አቶ አርከበ ይዞ ብቅ ያለው መቀስቀሻ የካድሬውን እና አባሉን ቁስል የነካ በመሆኑ ተቀባይነት አገኘ፡፡ በትግራይ ፕሮፓጋንዳ እና ድርጅት ተመድበው የሚሰሩ ቁልፍ ካድሬዎች ተቀላቀሉት፡፡” (ገፅ 26)

ይህንን ተከትሎ ወትሮም በደፋር ንግግሯ የምትታወቀውና አንጋፋ ታጋዮችን ሳይቀር በቁጣ የምታስረግደው ቀዳማዊት እመቤት የሰነዘረችው የመልስ ምት በመጽሐፉ ላይ እንደሚከተለው ሰፍሯል፡- “ወ/ሮ አዜብ በበኩሏ አርከበና ቡድኖቹ በሙስና ተዘፍቀዋል የሚል ክስ ይዛ ብቅ አለች፡፡ አርከበ በሚስቱና ቤተሰቦቹ የያዘውን ንብረት በመረጃ አስደግፋ አራገበች፡፡ ላውንደሪ ቤት፣ ፋርማሲ፣ ክሊኒክ፣ ሱፐር ማርኬት፣ መስታወት ማስመጣትና መሸጥ…፡፡ በትግራይና አዲስ አበባ የተፈጠሩት አዳዲስ ባለሀብቶች የአርከበና ቡድኖቹ እንደሆኑ በስም ዘርዝራ አሳወቀች፡፡ ስዬ በታሰረበት የሌብነት ወንጀል አርከበ እጁ እንደነበረ፣ በተለይም የስዬ ወንድም ለገዛቸው በርካታ መኪናዎች ቅናሽ እንዲያገኝ ማግባባቱን የፈፀመው አርከበ መሆኑን አጋለጠች፡፡” (ገፅ 26)

እዚህ ጋ አቶ ኤርሚያስ ‹‹አርከበ በሚስቱና በቤተሰቦቹ…›› ስለያዛቸውና አዜብ መስፍን በስም እየጠራች አጋለጠች ስላላቸው የንግድ ድርጅቶች በስም አንድ በአንድ እየጠቀሰ ይፋ ቢያደርግልን ኖሮ መረጃው ምሉዕ (ከ‹ኮሪደር ሀሜት› የዘለለ) ይሆን ነበር ብዬ አስባለሁ፡፡ ከሁሉም ቁጭታችንን የሚያንረው፣ ደራሲው የንግድ ተቋማቱን ባለቤቶች በስም መጥቀስ እየቻለ (አቀራረቡ ለይቶ እንደሚያውቅ ያሳብቃልና) በደፈናው ያለፈው ወንጀል (ሕገ-ወጥ ዘረፋ) ይህ ብቻ አለመሆኑ ሲገባን ነው፤ በዚሁ ገፅ ዝቅ ብሎ የሰፈረው እንዲህ ይላልና፡- “በወቅቱ ሁለቱም ቡድኖች ‹ያለ ኢኮኖሚ የበላይነት፣ የፖለቲካ የበላይነት አይመጣም› የሚል ፖሊሲ ቀርፀው የህወሓት ባለሀብቶችን ለመፍጠር ተንቀሳቅሰዋል፡፡ በዚህ ፖሊሲ ምክንያት በአንድ ሌሊት ከሹፌርነት ወደ አስመጪና ላኪነት፣ ከጋራዥ ሰራተኛነት ወደ መኪና ዕቃ መለዋወጫ አስመጪነት፣ ከታጋይነት ወደ ሪል እስቴት ባለቤትነት፣ ከወታደርነት ወደ ፋብሪካ ባለቤትነት፣ ከህወሓት ምድብተኛ ካድሬ ወደግል ባንክ ከፍተኛ አክሲዮን ባለድርሻነት የተቀየሩ ሰዎችን መስማት የተለመደ ነበር፡፡” (ገፅ 26) እነዚህ ‹‹ተላላኪ›› እና ‹‹ሹፌር›› ባለሀብቶችን በስም አለመጥቀሱ ያስቆጫል፤ በተለይም ለመረጃው ከነበረው ቅርበት አኳያ ይሄ ጉዳይ እንደተራ ነገር በደፈናው ባይታለፍ ኖሮ፣ ለተቃውሞው ስብስብ በዋናነት ሁለት ታላላቅ የፖለቲካ ትርፍ ማስገኘቱ አይቀሬ ነበር፡፡

የመጀመሪያው በጅምላ ህወሓት፣ መላው ትግሪኛ ቋንቋ ተናጋሪን ተጠቃሚ ያደረገ የሚመስለው ኢትዮጵያዊ ስህተቱን እንዲያጠራ ስለሚያስችለው፣ በድርጅቱ እና በብሔሩ መሀከል ያለውን ነጭና ጥቁር ልዩነት እንዲያስተውል ይረዳው ነበር፤ ሌላው ደግሞ እነዚህን በፖለቲካ ውሳኔ ወደሀብት ማማ የወጡትን ግለሰቦች የትላንት ማንነት አብጠርጥሮ የሚያውቀው ቤተሰብ፣ ጎረቤት፣ ዘመድ አዝማድ… የዘረፋ ወንጀላቸውን ተፀይፎ በኢኮኖሚያዊ ማግለል (ሸቀጦቻቸውን ባለመግዛትም ሆነ አገልግሎታቸውን ባለመጠቀም) በተቃውሞ ጎራ እንዲሰለፍ ገፊ-ምክንያት ይሆነው ነበር የሚለው ጭብጥ ነው፡፡ ‹‹የመለስ ትሩፋቶች›› መጽሐፍ በሀገሪቱ ውስጥ ከመጋረጃው ጀርባ ስለተፈፅሙ ህልቆ-መሳፍርት ያሌላቸው አሳፋሪ የህወሓት ሕገ-ወጥ ድርጊቶች እና እብሪቶችን ተንትኖ አስነብቦናል፡፡ ከእነዚህ መሀልም የስምንቱ ኮሎኔሎች ‹‹ጀብድ››ን እዚህ ጋ መጥቀሱ አግባብነት አለው ብዬ አምናለሁ፤ ከ268-269 ባሉ ገፆች እንደተተረከው፣ በምርጫ 97 ማግስት በአንዱ ዕለት በወታደራዊ የደንብ ልብስ የተንቆጠቆጡ ስምንት ከፍተኛ መኮንኖች በሶስት ሄሌኮፕተር ተሳፍረው አሮጌው አውሮፕላን ማረፊያ ይደርሳሉ፤ በቀጥታም የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ከንቲባ ወደነበረው አባተ ስጦታው ቢሮ በማምራት፣ መሬት እንደሚሰጥ መረጃ ደርሷቸው ከጦር ግንባር እንደመጡ ይነግሩታል፤ እያንዳንዳቸውም ‹‹ዘመቻ ፀሀይ ግባት የቤት ማሕበር››፣ ‹‹ኃየሎም አርአያ የቤት ማሕበር››፣ ‹‹ዛላአንበሳ የቤት ማሕበር››… የሚል እና መሰል የማህደር ስያሜ ያላቸው የአስራ ሁለት መኮንኖች ስም ዝርዝርና ፊርማ የያዘ ወረቀት ይሰጡታል፤ እንደ ብራ መብረቅ ድንገት ባጋጠመው ክስተት ክፉኛ የተረበሸው ከንቲባም እንዲህ ያለ መመሪያ እንዳልወረደ ለማስረዳት ሲሞክር፣ ለዚህ ዓይነቱ እሰጥ-ገባ ጊዜ ያልነበራቸው የጦር አበጋዞቹ አብረቅራቂ ሽጉጦቻቸውን በመምዘዝ ግንባሩ ላይ ደቅነው በወቅቱ ፋሽን በነበረው ኢህአዴጋዊ ፍረጃ ‹‹የቅንጅት ተላላኪ መሆንህን ደርሰንበታል››፣ ‹‹ኢህአዴግ እንዲሸነፍ ያደረጋችሁት እንዳንተ ያሉ ሰርጎ-ገቦች ናቸው››፣ ‹‹እዚሁ ደፍተንህ እንሄዳለን››… የሚሉ ማስፈራሪያዎችን አዥጎድጉደው በማስጠንቀቅ ነፍስ-ውጪ፣ ነፍስ ግቢ ወጥረው ይይዙታል፤ ይህን ጊዜ የህወሓት አባል የሆነው ምክትል ከንቲባው ነጋ በርሔ፣ የአባተን ቢሮ በርግዶ ሳይታሰብ ዘው በማለቱ፣ አንደኛው ኮሎኔል ያነጣጠረውን መሳሪያ ከአይን በፈጠነ ቅፅበት አዙሮ ይደቅንበታል፡፡ ሁኔታውን ከጉዳይ ያልጣፈው ነጋ በርሔም ባለሽጉጦቹን የጦር አበጋዞች በባዶ እጁ እንዲህ ሲል ተጋፈጣቸው፡-
“ነፍጥ ከእናንተ በፊት አንግበን ተራራ ደርምሰናል፡፡ የምታስፈራሩትን ሂዱና ሌላ ቦታ አስፈራሩ!”

ከፍተኛ መኮንኖቹም በድንጋጤ መሳሪያዎቻቸውን በመዘዙበት ፍጥነት ወደአፎቱ መልሰውና የምክትል ከንቲባውን የስድብ ውርጅብኝ በፀጥታ አዳምጠው ሲያበቁ፣ አባተን ይቅርታ እንዲጠይቁት ይታዘዛሉ፤ እንዲያ በጥንካሬያቸው ለማንም የሰው ልጅ የማይበገሩ መስለው ሲንጎማለሉ የነበሩት ቆፍጣናዎቹ ኮሎኔሎች ባንዴ እንደፊኛ ተንፍሰው በፍርሃት የታዘዙትን ይፈፅማሉ፤ ከዚህ በኋላም ህወሓቱ ነጋ በርሔ በተረጋጋ አንደበት ዋናው ከንቲባውም ጭምር እንዲሰማ ድምፁን አጉልቶ የሚከተለውን ‹‹ምርጥ›› ምክር ለገሳቸው፡ –
“ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ጥያቄያችሁን ብታቀርቡ ኖሮ አባተ እንኳን ቤተሰባችሁን ጥላችሁ ግንባራችሁን ለጥይት ለምትሰጡት ቀርቶ ለሌላውም አይጨክንም፡፡ ያውም ከቀናት በኋላ ጠላት (ቅንጅት) ተረክቦ ለሚዘርፋት አዲስ አበባ!” (ገፅ 255) ከንቲባውም መሬቱን ፈቀደ፤ ነጋም ወደ መቀሌ እንዲዘዋወር ተደርጎ፣ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴን እና የትግራይ ክልል ካቢኔን ተቀላቀለ፤ ከጊዜ በኋላም በበረከት ስምዖን በተመራ ግምገማ ላይ በአስቸኳይ አዲስ አበባ መጥቶ ይህንን ጉዳይ እንዲያስረዳ ቢጠየቅ አሻፈረኝ ብሎ ይቀራል፡፡ ደራሲውም ‹‹ዘመን አለፈና አዲሱ ለገሰን ለማገዝ ኢህአዴግ ቢሮ የሥልጠና ማዕከል በምክትል ሚኒስትርነት ማዕርግ ተመደበ›› ሲል የሆሊውድ ፊልምን የሚያስንቀውን ታሪክ ይደመድማል፡፡ በርግጥ አባተም ቢሆን ይህ አስፈሪ ገጠመኙ እንደድንቅ ቃለ-ተውኔት ሁሉ፣ በህወሓት መሪዎች ተደርሶ በኮሎኔሎቹ እና በነጋ የተተወነ መሆኑን ለመረዳት በርካታ ወራት እንደፈጀበት
ተጠቅሷል፡፡

በሌላ ምዕራፍ ደግሞ፤ በምርጫው ቀን እኩለ ሌሊት ተቋቁሞ፣ በአርከበ እቁባይ እና በጄነራል ታደሰ ወረደ እንዲመራ የተደረገው ‹‹የፖለቲካ ፀጥታ ጥምር ኮሚቴ››፣ ከ1978 ዓ.ም በፊት ወደ ትግል የገቡና ማዕረጋቸው ከኮሎኔል በላይ የሆነ የህወሓት መኮንኖች ቦሌ ላይ መሬት እንዲያገኙ ማመቻቸቱን አስነብቦናል፡፡ በአናቱም፣ ከኮሎኔል በታች ያሉ የህወሓት ታጋዮች በሌሎች ማስፋፊያ ከተሞች መሬት ማግኘታቸውን ተከትሎ የተፈጠረውን ሁኔታ ሚኒስትር ዴኤታው እንዲህ ያወጋናል፡- “…ወሬው ባድመና ጾረና ጦር ግንባር ድረስ ተዳረሰ፡፡ ወታደራዊ መኮንኖቹ ምሽጋቸውን እየለቀቁ በጦር ሂሊኮፕተሮች ጭምር እየተሳፈሩ አዲሳባን ወረሯት፡፡ የክፍለ ከተሞች ግቢ አቧራ በጠጣ የኮከብ ጋሻና ጦር ክምር የተሸከመ ካኪ ተጥለቀለቀ፡፡” (ገፅ 255-256) ዘመነኛው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ‹‹…አንዳንድ እንሰሳት ይበልጥ እኩል ናቸው›› በሚል ያልተፃፈ ሕግ ማደሩን ከውስጥ-አወቅ ምስክርነት የምንረዳው ከህወሓት ውጪ ያሉት ኢህአዴግን የመሰረቱ ድርጅቶች የአመራር አባላት ብቻ የወሰዷትን መሬት በግምገማ እንዲመልሱ መገደዳቸው በዚሁ መጽሐፍ መስፈሩን ስናስተውል ነው፡፡ በወቅቱም በግምገማው ፊት-አውራሪ በረከት ስምዖን የተዘጋጀ ‹‹ከምርጫው በኋላ የድርጅታችንን ስም ያጎደፉና የሕዝቡን ቅሬታ ያባባሱ ተግባራት›› የሚል ሃያ ገፅ ሰነድ የመነሻ ሃሳብ ሆኖ ቀርቦ ነበር፤ የግምገማው ውጤትም የተዘረፈ መሬት ማስመለሻ ፎርምን ህወሓት ያልሆኑ ከ600 በላይ የኢህአዴግ ካድሬዎች እንዲሞሉ አስገድዶ ተጠናቅቋል፡፡

ለአብነትም ደራሲው ‹‹ለታሪክ የተቀመጠው የይቅርታ ፎርም›› ብሎ በመጽሐፉ ያሰፈረውንና በአንድ የብአዴን አመራር የተሞላውን እንደወረደ ልጥቀሰው፡- “ለቦሌ ክፍለ ከተማ መሬት አስተዳደር እኔ ህላዊ ዮሴፍ ድርጅቴ ኢህአዴግና መንግስት የጣለብኝን አደራና ኃላፊነት ወደጎን በመተው ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ የመሬት ወረራ ላይ በመሰማራት አንድ መሬት ወስጃለሁ፡፡ በመሆኑም ይህን ያለአግባብ የወሰድኩትን መሬት አስተዳደሩ እንዲረከበኝ በማክበር እጠይቃለሁ፡፡ ድርጅቴ ኢህአዴግና በእሱ የሚመራው መንግስትም ይቅርታ እንዲያደርግልኝና ከእንግዲህ ወዲያ በየትኛውም የድርጅቴንና የመንግስት ስም በሚያጎድፍ ተግባራት ላለመሰማራት ቃል እገባለሁ፡፡
ከሰላምታ ጋር ህላዊ ዮሴፍ
ግልባጭ
ለአዲስ አበባ ጊዜያዊ ባለአደራ አስተዳደር
ለቦሌ ክፍለ ከተማ ጊዜያዊ ባለአደራ አስተዳደር
ለኢህአዴግ ጽ/ቤት” (ገፅ 257)
የሆነው ሆነ ኤርሚያስ ለገሰ በዚህ መጽሔት ላይ እንዲህ በቀላሉ ጠቅሰን የማንጨርሳቸውን በርካታ አይን ያወጡ ድርጅታዊ እና ግለሰባዊ ዘረፋዎችን ልባችን ቀጥ እስኪል ድረስ አስነብቦናል፡፡ ሌላው ቀርቶ ዛሬ በየመድረኩ ‹ኢህአዴግ ጌታ ነው!›፣ ‹መለስ መሲህ ነው!›… አይነት ፕሮፓጋንዳ በማድመቅ ግንባር-ቀደም እየሆነ የመጣው ጀግናው አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ ራሱ የዘረፋው ተቋዳሽእንደነበረ እንዲህ ሲል ነግሮናል፡-

“ከሁሉም የሚያሳዝነው ሀገራችንን በዓለም መድረክ በማስጠራቱ የምንወደው ኃይሌ፣ በአስታራቂ ሽማግሌነቱ የምናመሰግነው ኃይሌ፣ በዓለም አደባባይ አልቅሶ ያስለቀሰን ኃይሌ ‹ኃይሌና አለም ሪል ስቴት› በሚል የድርጅት ስም በመስከረም 7/1998 ዓ.ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 18 ውስጥ 50,000 ካሬ ሜትር ሕጋዊ ሰውነት በነዋሪው ድምፅ ከተገፈፈው አርከበ እቁባይ እጅ ወስዷል፡፡ መቼም ታላቁ ሯጭ እየተካሄደ ያለው ውንብድና አዲስ አበባን ማጥፋት እንደሆነ ሳይገባው ቀርቶ አይመስለኝም፡፡” (ገፅ 400-401)

…የወዶ ተሳዳጁ የኦህዴድ ካድሬ፣ ከሁለት ዓስርታት በላይ ሲነገርና ሲፃፍ የነበረውን ርዕሰ-ጉዳይ ለማጠናከር በርካታ የመጽሐፉን ገጾች ሰውቷል፡፡ ይህ የህወሓት ብቸኛ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ጠቅላይነት ትርክት፣ ገዢ የተቃውሞው መከራከሪያ መሆኑን በሚገባ የሚያውቀው ኤርሚያስ፣ በተለይም ባገለገለበት አዲስ አበባ ዙሪያ ያልተገለጡ የሚመስሉ ሁነቶችን አስተሳስሮ ለመተረክ ጥሯል፡፡ በርግጥ ለእግረ-መንገድ ያህል አንድ ጥርጣሬ ጥለን እንለፍ፤ ይህን መስመር አብዝቶ ማብራራት፣ ተደማጭነትን እና የፖለቲካ ሁለተኛ ዕድልን እንደሚሰጥ ሚኒስትሩ ከመረዳቱ አኳያ፤ የተባሉትን በምልዐት መቀበሉ ጥቂትም ቢሆን አስቸጋሪ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ አልፎም፣ የትግሪኛ ተናጋሪውን እና ህወሓትን ቀላቅሎ ወደመመልከት እንዳያሻግረን ብርቱ ጥንቃቄ ማድረጉም ሊታወስ ይገባል፡፡

(በሚቀጥለው ሳምንት ይህንኑ መጽሐፍ በማጣቀሻነት እያወሳን፣ የህወሓትን የፖለቲካ የበላይነት እና ጠቅላይነት የሚያሳዩ ወጎችን እንዳስሳለን)

የህወሓት ትውልድ ገዳይ ስውር መርዝ

$
0
0

አሁን እጅግ በላቀ የዕድገት ደረጃ ሆኖው የሚናያቸው የአለም አገራት መሰረታቸው እውቀት ነው::ያለ እውቀት ፈጠራና ምርምር÷ጥበብና ክህሎት÷ዕድገትና ልማት ሊኖሩ አይችሉም::
ትምህርት የእውቀት ቤት ነው:: እውቀት ካለ ደግሞ ምክንያትነት አለ:: ምክንያትነት ካለ ደግሞ ምርምርና ጥናት አለ::ምርምር ካለ ደግሞ መጠየቅ አለ:: መጠየቅ ካለ ደግሞ መከራከርና መወያየት አለ:: መከራከር ካለ ደግሞ የለውጥ መንገድ አለ:: የለውጥ መንገድ ካለ ደግሞ ዕድገት አለ!!!!
ህወሓት ገና በረኻ ደደቢት እያለች 1973 “የወደፊት የኔ ጠላት ሙሁሩ ክፍል ነው” ማለቷም “የኔ ጠላት ዕውቀት ነው” ከሚል ሐሳብ ጥልቅ የሆነ ግንኙነት አለው::በአሁኑ ዘመን ትምህርት ምላሷ እንጂ ተክለ ሰውነቷ(ቁመናዋ) የለም ማለት ይቻላል:: ይህ ማለት ደግሞ የዕውቀት ግንብ ፈርሷል ማለት ነው::ይህ ማለት ደግሞ የጥበብና የምርምር ቤት ተንዷል ማለት ነው::ይህ ማለትም ምክንያታዊ አስተሳሰብና ግንዛቤ ቀብሮ አገርን ያለ ጠያቂና ተጠያቂ በማስቀረት የለውጥ ድልድይ እንዳይሰራ ያደርጋል::አሁን እያየነው ያለነውም ይህ ነው::
በህወሓት ዘመነ ስልጣን ብዙ ሙሁራን ደብዛቸውን ጠፍቷል::ወህኒ ቤት(ጓንታናሞ) ወርዷል::አገራቸውን ለቀው በባዕድ አገር ሰፍሯል::ይህ ማለት ደግሞ የህወሓት/ኢህአዴግ የዕቀት ጠላትነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ መስታዎት ነው::

ህወሓት በእውነት ለኢትዮጵያ ዕድገት ከልብ የሚቆረቆር ቢሆን ኖሮ አሁን ያለው እጅግ የሞተ የትምህርት ጥራት አስተካክሎ ትውልድን የዕውቀት ባለቤት አድርጎ የምርምር ማዕበል በመክፈት ለውጣዊ የዕድገት መንገድ መስራት በቻለ ነበር:: ዳሩ ግን ይህ አይደለም::
የህወሓት ዋና አለማ ከጅምሩ የትምህርት ጥራትን በማበላሸት የትውልድ የእውቀት ጥይትን በመቅበር አገር ያለ ምንም ጠያቂና ተጠያቂ በማስቀረት ዘላለማዊ አምባገነናዊ ስልጣን መቆናጠጥ ነው::ይህ እባባዊ ጥቁር ሴራ “ለህዝብ ኑሮ ለህዝብ የሞተ አገራዊ÷አህጉራዊና አለማዊ ምጡቅ መሪ”እየተባሉ የተሞካሹ የአቶ መለስ ዜናዊ ነው:: አቶ መለስ ዜናዊ የትውልድ የእውቀት ጥይት ለመቅበር የእውቀት አባት የሆኖውን ‘መምህር’ ክብሩን ዝቅ አድርገው በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ በማያቅ አኳሃን አድቅቀውና አመንምነው አረከሱት::የእኝህ ሰው ታላቁ ጥቁር አስተሳሰብም መነሻው ይህ ነው::ትውልድ ገዳይ ስውር መርዝም ይህ የእውቀት ጠላትነት ነው!!
በአሁኑ ዘመን መምህርና ትውልድ ላይገናኙ አብረው እየተራመዱ ነው::እውቀትና ትውልድም በጣም ተራርቋል::የዕውቀት ድልድይ ተንዳለች::የትውልድ አስተሳሰብም በእጅጉ ወርዷል::የለውጥ ሻማም ጠፍታለች::

ኢትዮጵያ የትምህርት አብዮት ያስፈልጋታል::የዕውቀት አብዮት ያስፈልጋታል::የጥበብና የምርምር አብዮት ያስፈልጋታል::የባህል አብዮት ያስፈልጋታል::ይህን ሳታደርግ ዕድገት ልታመጣ አትችልም::ኢትዮጵያ በድንጋይ ሳይሆን በእውቀት መገንባት አለባት::በምላስ ሳይሆን በተግባር መገንባት አለባት::በዘፈቀደ ሳይሆን በምርምርና በጥበብ መገንባት አለባት::
ህወሓት በአሁኑ ጊዜ የት እንደነበረ÷አሁን የት እንዳለ÷ለወደፊት ወዴት እየሄደ እንዳለ በእውን ለይቶ የማያቅ የምክንያታዊ አስተሳሰብ መኸን ትውልድ እያፈራ ይገኛል:: ይህም ዛሬ ኢትዮጵያ በካድሬው÷ ነገ ደግሞ በካድሬው ልጆች መመራቷ የማይቀር ነው ማለት ነው::
ይህ የህወሓት ጥቁርና የማይረባ አጉል አስተሳሰብ(የእውቀት ጠላትነት) እስካልተወገደ ድረስ “ኢትዮጵያ መካክለኛ ዕድገት ካላቸው አገራት ትቀላቀላለች” ማለትም ከንቱ ምኞት(ቅዠት) ከመሆን የሚያልፍ አይደለም::………..

tplf

የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች መስከረም 23 ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

$
0
0

blue_party_ethiopia101370869814 (1)በሽብርተኝነት ተከሰው ማዕከላዊ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ የጋሞጎፋ ዞን አመራሮች መስከረም 23/2007 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ 8፡00 አራዳ ችሎት እንደሚቀርቡ የሰማያዊ ፓርቲ የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ የጋሞጎፋ ዞን ምክትል ሊቀመንበር አቶ ፍቃዱ አበበ እንዲሁም የዞኑ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ኢንጅነር ጌታሁን አርባምንጭ ውስጥ ወር ከ15 ቀን ያህል ታስረው የነበር ሲሆን ወደ ማዕከላዊ ከተዛወሩ ሁለት ሳምንት እንደሆናቸው የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊው ገልጸዋል፡፡

ታሳሪዎቹ በቤተሰብ፣ በኃይማኖት አባትና በጠበቃ እንዳይጠየቁ የተከለከሉ ሲሆን የምክትል ሊቀመንበሩ አቶ በፈቃዱ ባለቤትና አባት እንዳይጠይቁ መከልከላቸውን ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል፡: (ነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ)

ኢትዮጵያ ያለባት የብድር መጠን 400,000,000,000 (አራት መቶ ቢልዮን ብር) ወይንም 20,000,000,000 (ሀያ ቢልዮን ዶላር ደርሷል)

$
0
0
የታዳጊ ሀገሮች ወደ ውጭ የሚወጣው የገንዘብ ፍሰት እ ኤ አ ከ2001-2010 ዓም (የካርታውን ምንጭ ለማግኘት ይህንን ይጫኑ 

gudayachinበሀገር ስም መበደር ትንሽ ለባቡር፣ለመንገድ እና ለፎቅ መስርያ ማዋል፣ ከተማውን ሞቅ ማድረግ፣ የድሆችን ቤት እያፈረሱ ከከተማ ማራቅ እና   የቀረውን አብዛኛውን በብድር የተገኘ ገንዘብ ግን በሙስና ለግል ጥቅም ማዋል አልያም በውጭ ባንኮች በግል ስም ማስቀመጥ።በመጨረሻም የብድር ዕዳውን ለልጅ ልጅ ማቆየት።ኢትዮጵያ ያለባት የብድር መጠን  400,000,000,000 (አራት መቶ ቢልዮን ብር)ወይንም 20,000,000,000 (ሀያ ቢልዮን ዶላር ደርሷል)።

አስገራሚው ነገር የብድር ስምምነቶችን ማፅደቅ ያለበት የሀገሪቱ ምክርቤት ሲሆን በአሁኑ ትውልድ እና በመጪው ትውልድ ስም እየተበደረ ያለው መንግስት በይስሙላ ምክርቤቱ የሚያፀድቀው ለፎርማሊቲ መሆኑ ነው።
የኢትዮጵያ ቴሌቭዥንም ሆነ ባለስልጣናት ኢትዮጵያ ብድር ስታገኝ እንደ ትልቅ ስኬት እየተኩራሩ ነው የሚነግሩን።በመሰረቱ አንዲት ሀገር ከሀገር ውስጥ ምርቷ እና ከውጭ ንግድ ገንዘብ አግኝታ ልማት ስትሰራ እንጂ ተበድራ ለትውልድ በምታቆየው የብድር ዕዳ  ”ልማት ተሰራ” ብላ መኩራራት አትችልም።ምክንያቱም በብድር የመጣው መዋለ ንዋይ በራሱ አትራፊ መሆኑ የሚታየው ከአመታት በኃላ ያውም ብዙ ነገሮች ባሉበት የመሆናቸው ዕድል ከተፈጠረ በመሆኑ ነው።

የዶላር በብር አንፃር ያሳየው የምንዛሪ እድገት (ከጉግል የገንዘብ ምንዛሪ መረጃ የተገኘ)

ዛሬ አንድ ሰው ተበድሮ ጥሩ ሊለብስ፣ሊንቆጠቆጥ ይችላል።ነጥቡ ግን ተበድሮ ነው? ወይስ ሰርቶ ነው ያማረበት ነው? የአዲስ አበባን የባቡሩ ዝርጋታ ጉዳይ ስናስብ እንዲህም እናስባለን።በአሁኑ ትውልድ እና በመጪው ትውልድ ስም ተበድረን ”እኔ ከሞትኩ ” በሚል መርህ ይመርብን? ወይንስ ማማራችንን በልክ አድርገን ሰርተን ለማግኘት ጥረን በሀገር ምርት እና በውጭ ንግድ በምናገኘው ሀብት  ሀገራችንን እናሳድግ? ይህ ነው የሀገር መሪዎች ፈታኝ ጥያቄ።የእኛን የከፋ የሚያደርገው ተበድረንም አብዛኛው ከሀገር በህገወጥ መንገድ መመዝበሩን መስማታችን ነው።

ኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት በለየለት የገንዘብ ዘረፋ ላይ መሰማራታቸውን እራሱ መንግስትም ያመነው ጉዳይ ነው።አንዳንድ ባለሥልጣናቱንም ዘብጥያ ማውረዱ ይታወቃል።ሆኖም የኢትዮጵያ አንጡራ ሃብት በቢልዮን የሚቆጠር ዶላር አሁንም እየተመነዘረ መውጣቱ የዓለም ዓቀፍ ጥናቶች አመላክተዋል።የሚገርመው ነገር ግን እንደተጠበቀው የሙስና ዘመቻ ሲባል የነበረው የውሃ ሽታ ሆኖ መቅረቱ ነው።አሁን የሙስና ኮሚሽን መኖሩን የሚያስታውሱት ምናልባት በለጋሃር በኩል ሲያልፉ ህንፃውን ከተመለከቱ ብቻ ነው።

ጥቂቶች በናጠጡበት፣ ሙስና ከሃይማኖት ድርጅት እስከ ቁንጮ ባለስልጣናት የተካኑበት ተግባር ነው። ጉዳዩ የበለጠ የእያንዳንዱን ሰው ትኩረት የሚሻ መሆኑን የምንረዳው ሀገሪቱ በገፍ ከውጭ ከሚቀርበው እርዳታ በተጨማሪ በከፍተኛ መጠን እየገባችበት ያለው የብድር ዕዳ ነው።በአግባቡ በፓርላማ የማይመከርባቸው፣ ፓርላማ ላይም ቢነሳ ሁሉም አጨብጭቦ የሚወጣበት ፓርላማ ከመሆኑ አንፃር ብድሩን የሚያፀድቀው አካል ምን ያህል ኃላፊነት እየተሰማው ነው? የሚለው ሌላው አጠያያቂ ጉዳይ ነው።ዕዳው ለልጅ ልጅ የሚቀመጥ እየተቀመጠልን መሆኑን አለመዘንጋት ጠቃሚ ነው።

የኢትዮጵያ የገንዘብ እና ኤኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ድረ-ገፅ እንደሚያመለክተው በ 2001 እና በ 2005 ዓም መካከል ባሉት ዓመታት ብቻ  የኢትዮጵያ የውጭ ብድር በ 156 % ማደጉን ያሳያል።ይሄውም በ 2001 ዓም 4.35 ቢልዮን የነበረው ብድር በአምስት ዓመታት ውስጥ ወደ 11.17 ቢልዮን ዶላር መመንደጉን ያሳያል።ባጠቃላይ የቅሌት መዝገባችን ወደ 16.11 ቢልዮን ዶላር ደርሷል። አብዛኞቹ በመንግስት የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ዋና ምንጫቸው የውጭ ብድር ነው።ብድር አትራፊ ለሆኑ አዋጭ ፕሮጀክቶች ከሆነ ሙሉ በሙሉ አይወቀስም ነገር ግን ተበድሮ ለሙስና እና ለጥቂቶች ኪስ ማድለብያ ሲሆን ወንጀሉን ያከብደዋል።

ሚያዝያ 2/2006 ዓም የ ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ባቀረበው የአምስት ዓመት ትራንስፎርሜሽን ክንውን ላይ ከተባለው ግብ ኢትዮጵያ መድረስ አለመቻሏን አምኗል። የምክር ቤቱ ብቸኛ ተቃዋሚ አቶ ግርማ ”ቀድሞውንም ዕቅዱ በአግባቡ ያልታሰበበት ለመሆኑ አሁን ላለበት ውጤት መብቃቱ በራሱ ምስክር ነው” ብለዋል።

የኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት ከፖሊሲ ችግር በተጨማሪ ቅጥ ያጡ የኢህአዲግ ባለስልጣናት ሙስና ዋነኛው ምክንያት ለመሆኑ አያጠራጥርም። ከእነርሱ ጋር አብረው የሚዘርፉ ግን ሀገሪቱ አድጋለች እያሉ ሪፖርት ለማውጣት የሚሽቀዳደሙ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችን እዚህ ላይ መዘንጋት አይገባም።

ከላይ መግስት እራሱ  ያመነውን የብድር መጠን ካወሳን ቀጥለን ለሙስናው ማስረጃ ባለፈው ዓመት ግንቦት ላይ መሰረቱን ዋሽግተን ላይ ያደረገው ”ግሎባል ፋይናንስ እንተግርቲ” ከኢትዮጵያ  ባለፉት አስር ዓመታት ውስጥ በሕገ ወጥ መንገድ 16.5 ቢልዮን ዶላር ከሀገር ወጣ ይላል።(Ethiopia lost 16.5 Billion to illegal smuggling of cash out of the country in 10 years) ለትውልድ ከሚቀመጥ ብድር ላይ ከተሞች ሲብለጨለጩ እናይ ይሆናል።ግን ሀገሪቱ ከተበደረችው መጠን አንፃር እየተሰራ ነው ወይ? ስንል ትልቅ ጥያቄ ይጭራል። ጥያቄውን ይህንን ያህል ብድር የተበደረች ሀገር ዋና ከተማዋ ነዋሪ ከ25% በላይ የሚሆነው ውኃ ማግኘት አልቻለችም ይህም ቁጥሩ ወደ አንድ ሚልዮን የሚጠጋ ሕዝብ ነው።

ጉዳያችን
መስከረም 12/2007 ዓም (ሴፕቴምበር 22/2014)

 

በሽብርተኝነት ተጠርጥረው በእስር ላይ የቆዩት የዓረና ፓርቲ አባልና ሌሎች ግለሰቦች በ15 ሺሕ ብር ዋስ ተለቀቁ

$
0
0

ላለፉት ሦስት ወራት በሽብርተኝነት ተጠርጥረው በእስር ላይ የቆዩት የዓረና ፓርቲ አባል ወ/ሮ አልጋነሽ ገብሩና ሌሎች ስድስት ግለሰቦች እያንዳንዳቸው በ15 ሺሕ ብር ዋስ ተለቀቁ፡፡

የመቐለ ምንጮች ለሪፖርተር እንደገለጹት ከሆነ፣ ‹‹ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ በኃይል ለመናድ ተንቀሳቅሰዋል›› በሚል በሽብር ተጠርጥረው በእስር እንዲቆዩ የተደረጉት ወ/ሮ አልጋነሽ ገብሩ፣ አቶ ምዑዝ ፀጋይ፣ አቶ ሐለፎም ገብረ እዝጊ፣ አቶ አያሌው ጣዕምያለው፣ ቄስ ብርሃኑ ቆባዕ እና አንድ ስማቸው ያልተጠቀሱ ግለሰብ ባለፈው ማክሰኞ ከእስር ተለቀዋል፡፡

ግለሰቦቹ እግሪ ሐሪባ የተባለ በመቐለ ዙርያ የሚገኝ አንድ ገበሬ ማኅበር ቀበሌ ነዋሪዎች ሲሆኑ፣ ‹‹መንደሩ ወደ ከተማ ይቀላቀል አይቀላቀል›› በሚል በተፈጠረ አለመግባባት የክልሉን መንግሥት በመቃወማቸው ለእስር መዳረጋቸው መዘገቡ ይታወሳል፡፡

ከተወሰኑ የእስራት ቀናት በኋላ በዋስ ለማስለቀቅ ጥረት ቢደረግም፣ ከፍርድ ቤት በሽብርተኝነት መጠርጠራቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ የደረሳቸው ወ/ሮ አልጋነሽና ሌሎቹ ታሳሪዎች በእስር እንዲቆዩ ተደርጓል፡፡

ወ/ሮ አልጋነሽና ሌሎቹ ተጠርጣሪዎች እያንዳንዳቸው በ15 ሺሕ ብር ዋስ ቢለቀቁም፣ የአምስት ልጆች እናት የሆኑት ወ/ሮ አልጋነሽ ገብሩ ልጆቻቸው ደጋፊ አጥተው ችግር ላይ ወድቀው እንደነበር፣ ሕዝቡ ባደረገላቸው ድጋፍ ወደ ጎዳና ከመውጣት እንደታገደጋቸው ከዓረና ፓርቲ የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡

 Aleganesh-ID

Source:: Ethiopian Reporter

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live