Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ታጋይ ሞላ አስገዶም ከውጭ ጋዜጠኞች ጋር ያደረገው ቃለምልልስ (ቪድዮ)

$
0
0

የትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) ሊቀመንበር የሆነው ታጋይ ሞላ አስገዶም ከውጭ ጋዜጠኞች ጋር ያደረገው ቃለ-ምልልስ።
“አደረጃቻችን በብሄራችን ብንደራጅም ትግራይ ከሌሎች የኢትዮጵያ ህዝብ ለመለየት አይደለም፣ እንደ ስትራተጂ አንድነትዋ የተጠበቀ፤ የተጠናከረችና የብሄርብሄረሰቦች እኩልነት የተጠበቀባት፤ ፍትህ የነገሰባት አገር እንድትሆን ነው አለማችን። ስለዚህ በብሄራችን የመደራጀትና የትግራይ ህዝብ መባሉ እንደ ታክቲክ ነው እንጂ እንደ ስትራተጂ አይደለም። በዚ በመነሳት ትግላችን ሁሉም የኢትዮጵያ ብሄርብሄረሰቦች ያቀፈ በመሆኑ፤ በምናካሂደው ትግል ልዩነት የሚባል ነገር የለም። ከኛ ጋር አብረው መስዋእት እየከፈሉ ነው ያሉት።” ከቃለምልልሱ የተቀነጨበ። ሙሉውን ከቪድዮው፦


ታጋይ ሞላ አስገዶም ከውጭ ጋዜጠኞች ጋር ያደረገው ቃለምልልስ (ቪድዮ)


ዐይነ ስውር ድንጋይ ወርውሮ፣ ጠላቱን ስቶ ወዳጁን መታ!

$
0
0

“ምነው ወዳጅህ እኮ ነኝ፤ ቢለው”
“ዝም በል! ዋናው አለመሳታችን ነው!” አለው

ከዕለታት አንድ ቀን ሁለት ጓደኛሞች ጫካ ሄደው እንጨት ቆርጠው ለመምጣት ይፈልጋሉ፡፡ አንደኛው በመጥረቢያ ቅርንጫፍ እየቆረጠ ሳለ እጁና ሳያስበው ቆርጦ ጣለው፡፡ 
ጓደኝየው የተቆረጠውን ክንድ በፌስታል ውስጥ ከትቶ፤ እጁ የተቆረጠ ጓደኛውን ይዞ ወደ ቀዶ – ጥገና ሐኪም ወሰደው፡፡ 
ዶክተሩም – “በጣም ዕድለኛ ነህ እኔ የተቆረጡ አካላትን መልሶ የማጣበቅ ክሂል ባለሙያ ነኝ፡፡ በአራት ሰዓት ውስጥ ተመልሰህ ና” አለው፡፡ 
ጓደኝየው – “እሺ ዶክተር ባሉኝ ሰዓት እመጣለሁ” ይልና ይሄዳል፡፡ 
ከተባለው ሰዓት በኋላ ሲመለስ፤ ዶክተሩ፤ 
“እጨርሳለሁ ካልኩበት ሰዓት ቀድሜ ጨረስኩ፡፡ ገዋደኛህ ጤንነቱ ተመልሶ እዚህ ታች ወዳለው ግሮሠሪ ሄዷል፡፡”
ጓደኝየው በደስታ ጮቤ እየረገጠ ወደተባለው መጠጥ ቤት ሄደ፡፡ ጓደኝየው ጭራሽ የዳርት ውርወራ ግጥሚያ ይዟል፡፡ 
ከጥቂት ሣምንታት በኋላ ጓደኛሞቹ አሁንም ወደጫካ ሄደው እንጨት ቆረጣ ላይ ተሰማሩ፡፡ ባለፈው እጁን የቆረጠው ሰው አሁን ደግሞ እግሩን ቆርጦ ጣለው፡፡ ጓደኝየው እንዳለፈው ጊዜ የተቆረጠውን እግር ፌስታል ውስጥ ከትቶ ጓደኛውን ይዞ ወደዚያው የአካል ቀዶ ጥገና ሐኪም ዘንድ ይዞት ሄደ፡፡ 
ሐኪሙም፤ 
“አየህ፤ የእግር ቀዶ – ጥገና ትንሽ ከበድ ያለ ነው፡፡ ከስድስት ሰዓት በኋላ ተመለስ” አለው፡፡ 
ጓደኝየውም፤ 
“እንዳልከው አደርጋለሁ ዶክተር” ብሎ ሄደ፡፡ 
ከስድስት ሰዓታት በኋላ ተመልሶ ውጤቱን ለማወቅ ወደ ሐኪም ሲመጣ፤ 
ሐኪሙ “ይገርምሃል ከነገርኩህ ሰዓት አስቀድሜ ሥራ አገባደድኩ፡፡ ጓደኛህ እዚያ ታች ወዳለው እግር ኳስ ሜዳ ሄዶልሃል” አለው፡፡ 
ጓደኝየው ሐኪሙ አመስግኖ ወደ ኳስ ሜዳው ወርዶ ሲያየው፡፡ ያ እግረ የተገጠመለት ጓደኛው ምን የመሳሰሉ ጎሎች እያገባ ነው፡፡ 
ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ግን፣ ያ ጓደኝየው እጅግ ከባድ የመኪና አደጋ ይገጥመውና አንገቱ ሙሉ ለሙሉ ተቆረጠ፡፡ ጭንቅላቱ ብቻውን ወደቀ፡፡ 
እንደተለመደው የፈረደበት ጓደኛ ጭንቅላቱን በፌስታል ከትቶ ቀሪውን የጓደኝየውን አካል ጭኖ ወደ ሐኪሙ በረረ፡፡ 
ሐኪሙም፤ 
“ጭንቅላት መግጠም እጅግ ከባድ ነው፡፡ ለማንኛውን ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ተመለስ” አለው፡፡ 
ተመልሶ ሲመጣ፤ ሐኪሙ፡- 
“ይቅርታ አድርግልኝ፡፡ ጓደኛህ ሞቷል” አለው፡፡ 
ጓደኛውም፤ 
“ዕውነትክን ነው፡፡ የጭንቅላት ነገር ከባድ መሆኑን እገምታለሁ” አለ፡፡
ሐኪሙም፤
“ቀዶ ጥገናውን እንኳ ደህና አድርጌ ነበር የሰራሁት፡፡ ግን አየህ፤ አንተ ስታመጣው እዛ ፌስታል ውስጥ ታፍኖ ትንፋሽ አጥሮት ነው የሞተው!” 
*   *   *
እጅ እግሩን ከቆረጠበት አደጋ ያልተማረ፣ አንገቱን የሚቆረጥበት ሰዓት ይመጣል! ከስህተት አለመማር መዘዙ ራስን እስከማጣት ያደርሳል፡፡ 
የአካላችን ሁሉ አናት የሆነው ጭንቅላት የሁሉ ነገራችን መሪ ነው፡፡ አንዴ ካመለጠ የማይገጣጠም መሆኑም ይሄንኑ የሚያመላክተን ነው፡፡ ሁሉን ተግባራችንን በአቅል በአቅል የሚያስቀምጥልን፣ የሚያደራጁልን፣ መንገድ የሚያገባልን የህይወት መሪያችን እሱ ነው፡፡ በሀገር ደረጃ ሲታይም፤ ተቋሞቻችንን፣ ድርጅቶቻችንን፣ ት/ቤቶቻችንን፣ ኮሚሽኖቻችንን፣ ሚኒስቴሮቻችንን፣ ኢንዱስትሪዎቻችንን ወዘተ የሚመሩ ርዕሰ – አመራሮች እንደጭንቅላት ናቸው፡፡ የእነዚህ ጭንቅላቶች ልክ መሆን፣ ቅጥ መያዝና የድርና ማግ መቀናጀት ነው የሀገርን ጤና ልክነት የሚረጋግጠው፡፡ ይህ የጭንቅላት ክህሎት ከሌለ፣ ካልተባ፣ ከቀልብ ካልተዋሃደ ወጥነት ያለው አመራር ማግኘት አይቻልም፡፡ ጨርሶ ባዶ የሆነ ዕለት ደሞ መሄድ ቀርቶ መቆም ያቅታል፡፡ 
ገጣሚና ፀሐፌ ተውኔት ፀጋዬ ገ/መድህን፣ በ “በልግ” መጽሐፉ፤
“በዚህ በያዝኩት ጎራዴ፣ አንተግክን ቀንጥሼ ብጥለውም” 
ከባርኔጣህ በስተቀር፣ ዋጋ ያለው ነገር አይወድቅም”
የሚለን ለዚህ ነው 
“የዕውቀት ማነስ ፓለቲከኛ አደረገኝ” ከሚል ሰው ይሰውረን፡፡ አንዳንድ ፖለቲካ እጅግ አስመሳይ ከመሆኑ የተነሳ “የፆም መኪያቶ” “መኪያቶ” የሚባለውን ዓይነት ይሆናል፡፡ ወይ ሙሉውን መፆም ነው፣ አሊያ የሚለውን ሃሳብ ጨርሶ መርሳት ነው፡፡ “ፀብ ክርክር ካለበት ጮማ – ፍሪዳ፤ ፍቅር ያለበት ጎመን ይሻላል” ይላሉ አበው፡፡ በላሸቀ ኢኮኖሚ ውስጥ የፖለቲካ ጀግና መሆን እያደር ሽባ እንደሚያደርገን መገንዘብ ጭንቅላት ይዞ ማሰብን አይጠይቅም፡፡ ስለዚህ አስቀድሞ ኢኮኖሚውን ማዳን ነው፡፡ የዝሆን ጥርስ አናት ያለው ጉልላት ላይ ያለ የታችኛው ህዝብ መከራ አይታየውም፡፡ ያም ሆኖ የማይለወጥ ነገር የለም ሁሉም የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡ ወይም እንደ ቪክተር ፍራንክል፤ 
“ሁኔታዎችን መለወጥ ካልቻልክ ራስህን ለመለወጥ ትገደዳለህ” እንላለን፡፡ ቪክተር ከ2ኛው ዓለም ጦርነት ሆሎኮስት ቃጠሎ እልቂት የተረፈ ሳይካትሪስትና ፀሐፊ ነው፡፡ ከእልቂት ከተረፈ በኋላ በሰው ልጅ ላይ ምን ለውጥ እንደሚመጣ አስተውሏል፡፡ ለእያንዳንዱ ለውጥ ያ ሁሉ መስዋዕትነት መደገም አለበት ማለት አይደለም፡፡ ከማዕበሉ በኋላ የረጋ አየር፣ አየርም ቢሉ ለውጥ የሰፈነበት፤ ይመጣል ማለት እንጂ! 
የበላይም ይናገር የበታች ለሀገራችን የሚጠቅመው መደማመጥ ነው፡፡ በአንድ አቅጣጫ ብቻ እንደሚኬድበት መንገድ (One way road) አንሁን፡፡ የሚነገረንን እንስማ፡፡ ሌላው ሰው ድንገት ከእኔ የተሻለ ሀሳብ ቢያቀርብስ? እንበል፡፡ 
ደራሲ ከበደ ሚካኤል 
“አሁን የት ይገኛል ቢፈልጉ ዞሮ
መስማት ከማይፈልግ የባሰ ደንቆሮ”
ያሉትን አለመዘንጋት ከብዙ አባዜ ያድናል፡፡ እርግጥ ይህንንም የሚሰማ ካለ ነው፡፡ 
አበሻ በኢኮኖሚው መዘበትና ምፀት ማውራት ይችልበታል፡፡ ኢኮኖሚው አላፈናፍን ሲለው መውጫው በግጥም መተንፈስ ነው፡- 
“በቆሎ፤ በዝናብ፣ ሲጠብስ እያያችሁ
ሰዉ ሥራ አይሰራም፣ ለምን ትላላችሁ!”
የፖለቲካ ምፀት ሲያምረው ደግሞ፤ 
ዐይነ ስውር ድንጋይ ወርውሮ፣ ጠላቱን ስቶ ወዳጁን መታ፡፡
“ምነው? ወዳጅህን? ወዳጅህ ነኝ እኮ!” ቢለው፤
“ዝምበል፡፡ ዋናው አለመሳታችን ነው!” አለ ይባላል፤ ይላል፡፡ 

ምንጭ፥ –  አዲስ አድማስ

Comment

የኢህአዴግ ዲሞክራሲና የቴሌ ኔትዎርክ ተመሳሰሉብኝ

$
0
0

phone-towerእኔ የምለው … አንዳንድ የመንግስት ተቋማት በእነሱ ብሶ ለምንድነው ቁጣ ቁጣ የሚላቸው? (“የማይመቱት ልጅ ሲቆጡት ያለቅሳል” አሉ!) ከምሬ እኮ ነው… እኛ የተበደልነው አርፈን ተቀምጠን እነሱ እየተመላለሱ ይቆጡናል፡፡ (ኧረ “ፌር” አይደለም!) ያውም እኮ ሳንደርስባቸው ነው፤ ቤታችን ድረስ እየመጡ – በኢቴቪ መስኮት፡፡ ከሁሉም አንጀት የሚያበግነው ደግሞ ትላንት እኛው በድምፃችን ይመሩናል ብለን የመረጥናቸው ተወካዮቻችን፣ ማታ ማታ በቲቪ እየመጡ መቆጣታቸው ነው፡፡ (ለ90 ሚ. ህዝብ ማስጠንቀቂያ አይፃፍማ!) ይሄን ሁሉ ያስቀባጠረኝ የሰሞኑ የኢትዮ- ቴሌኮም ቁጣ የተቀላቀለበት መግለጫ ነው፡፡ (እኛ ሳንቆጣ እሱ ይቆጣን?!)
በእርግጥ መጀመሪያ የምስራቹን ነበር ያስቀደመው፡፡ ግዙፍ የማስፋፊያ ፕሮጀክቶቹን በስኬት ማጠናቀቁን በድል አድራጊነት ስሜት አበሰረን፡፡ (የቴሌ ድል የእኛም ድል ነው!) እንደመሰለኝ… የቁጣው መንስኤ የኢቴቪ ጋዜጠኛ ጥያቄ ነው፡፡ “ደንበኞች አሁንም የአገልግሎት ጥራት ችግሮች አሉ እያሉ ነው” የሚል ጥያቄ ሳያነሳ አልቀረም – ጋዜጠኛው፡፡ (ግን እኮ አልዋሸም!) ይሄኔ ነው ቁጣ ቁጣ ያለው – “አገልጋያችን” ኢትዮ-ቴሌኮም፡፡
አያችሁ… እዚህ አገር ሁሉ ነገር የተገላቢጦሽ ነው፡፡ በሌላው ዓለም ቢሆን እኮ የሚቆጣው ደንበኛ እንጂ አገልግሎት ሰጪው አይደለም፡፡ የሚቆጣው ህዝብ እንጂ መንግስት አይደለም፡፡ (መንግስትማ አገልጋይ ነው!) እኔ የምላችሁ… “ደንበኛ ንጉስ ነው” የሚለው አባባል እኛ አገር “ደንበኛ እርኩስ ነው” በሚል ተቀይሯል እንዴ? …በእርግጥ የኛ አገር ነጋዴዎች ወይም አገልግሎት ሰጪዎች “The Customer is always right” (ደንበኛ ሁሌም ትክክል ነው)  የምትለዋን አባባል ሲሰሙ “መስሎሃል!” እንደሚሉ ነገረ ስራቸው ያስታውቃል፡፡ እናም …ቢቆጡን፣ ቢያንገላቱን፣ መብራት ቢከለክሉን፣ ኔትዎርክ ቢነጥቁን፣ ውሃ ቢወስዱብን፣ ታክሲ የለም ቢሉን፣ ዘይት ቢያጠፉብን፣ ስኳር ቢያስወድዱብን፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ቢፈጥሩብን ወዘተ… ዝም ብለን መቀበል ብቻ ነው፡፡ ለምን “ደንበኛ ንጉስ”  ሳይሆን “እርኩስ ነው”
እናላችሁ… የኢትዮ ቴሌኮሙ ኃላፊ በኢቴቪ መስኮት ገጭ ብለው የመንግስት “የገቢ ኩራት” ስለሆነው መ/ቤታቸው ሽንጣቸውን ገትረው ተከራከሩ፡፡ የኔትዎርክ ማሻሻያው “ነዳጅ እንደሚበላ አሮጌ መኪና ሆነ” (አባባሉ የእኔ ነው!) ሲባሉ… አልካዱም፡፡ “በአንዳንድ አካባቢዎች አሁንም ኔትዎርክ ይጠፋል” የሚለውን ቅሬታም ተቀብለዋል፡፡ በመጨረሻ ግን “እናስ ምን ይጠበስ?!” ዓይነት ምላሽ ነው የሰጡት፡፡ “ይሄን ያህል ግዙፍ ፕሮጀክት ሲሰራ እኮ እንዲህ ዓይነት ችግሮች ያጋጥማሉ” አሉን፡፡ (ኔትዎርክ በዓመት አንዴ ጠፋ ብለን የምንሞላቀቅ “ቅንጡዎች”  አደረጉን እኮ!) በመካያውም… “የኔትዎርክም ሆነ ሌሎች ችግሮች በሂደት ይፈታሉ” … ብለው ገላገሉን፡፡ ይሄኔ ነው ኢህአዴግ ነፍሴ ትዝ ያለኝ፡፡ ኢህአዴግ ሁሌም ዲሞክራሲው ተንገራገጨ ወይም መልካም አስተዳደሩ ተሰናከለ አሊያም የሰብዓዊ መብት አያያዙ እያሳጣን ነው…በተባለ ቁጥር “በሂደት ይፈታል” ይለናል፡፡ የእሱ አይደለም የገረመኝ፡፡ የቴሌኮም መድገም ነው፡፡ (አወያይ መመሳሰል አሉ!)
ለዚህም ነው የኢህአዴግ ዲሞክራሲና የቴሌ ኔትዎርክ የተመሳሰለብኝ፡፡ (ሁለቱም የኋሊት ነው የሚጓዙት ልበል!) ለማንኛውም በሂደት ይፈታል ተብላችኋል – ኔትዎርኩ!!

ምንጭ፥ –  አዲስ አድማስ

‹‹አያ ጅቦ ሳታመኻኝ ብላኝ›› በበፍቃዱ ሃይሉ

$
0
0

‹‹ታዲያ ጥፋቴ ምንድን ነው ትላለህ?!››፣ ብሎኛል አንዱ መርማሪዬ ስለዞን ዘጠኝ እና እኔም እራሴ እንደጦማሪም እንደአራማጅ ተራማጅም ሠራሁ የምላቸውን ነገሮች ዝርዝር ነግሬው ሳበቃ፡፡ በኋላ ላይ በእስር ቤት ቋንቋ ከ‹‹አባሪዎቼ›› ጋር መገናኘት ከተፈቀደልን በኋላ ስንጠያየቅ ለካስ ሁላችንም ይቺኑ ጥያቄ ተጠይቀናል፡፡ ይኼ ነው እንግዲህ የምርመራችንን ሒደት የሚገልፀው ጥያቄ፡፡ ‹‹ተጠርጥረን›› የተያዝንበትን ጉዳይ የሚያረጋግጥ ሥራ ሠርተን ባለመገኘታችን (ወይም ‹‹ባለመናገራችን››) ታዲያ ጥፋትህ ምንድን ነው? ተባልን፡፡ ምርመራው የኛን ነፃ መሆን አለመሆን ለማጣራት ሳይሆን ጥፋት ለማግኘት ነበር፡፡ ብዙዎች ‹መንግሥት ዞን ዘጠኝን ለምን ሁለት ዓመት እንደታገሠው› ግራ በመጋባት ይጠይቃሉ፤ ባሕሪው አይደለምና፡፡ የኢትዮጵያ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነት ምኅዳር በቀላሉ እንደገመቱት ተይዘን፣ ተመርምረንና ‹‹ተገኘባችሁ›› የተባልነው ‹‹ የግንቦት 7 [እና ኦነግም ጭምር] አባልነት [ብሎም ግብ አስፈጻሚነት] ›› በሽታ ለተከሳሽነት አብቅቶናል፡፡ ቀጣዩ የክርክር ሂደት ነው፡፡
ከዚያ በፊት ግን ዞን ዘጠኝን በሩቅም በቅርብም የሚያውቁ በግራ መጋባት መልስ እንደሚሹ በማሰብ ይቺን አጭር ማስታወሻ ለመጻፍ ተገድጃለሁ፡፡ የእስራችን ሂደት ምን ይመስላል? የምርመራችንስ? እውን የግንቦት ሰባት አባል ነን? [ታዲያ] ለምን ታሰርን? በቅርቡ እንፈታ ይሆን?

ደቂቅም ይሁን ሊቅ ስለኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እውነታ የሚጽፍ ማንኛውም ሰው [ኢትዮጵያ ውስጥ ሳለ] አንድ ቀን እታሰር ይሆን እያለ መስጋቱ አይቀርም ፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም በአንድ መጽሐፋቸው ላይ ሰው ነገረኝ ብለው የኢትዮጵያ ሕዝብን በሦስት የመደቡት፡- የታሰረ፣ ታስሮ የተፈታ እና ወደፊት የሚታሰር በማለት፡፡ እርግጥ ዞን ዘጠኝ ‹‹ሐሳቡን መግለጽ ፈርቶ ዝም ያለ ሁሉ እስረኛ ነው›› ብሎ መደምደም ሦስቱም ምድብ አንደኛው ውስጥ ያጠቃልለዋል ‹‹የታሰረ›› በሚል፡፡ ዞን ዘጠኞች ጦማራችንን በከፈተን በሁለት ሳምንት ሲታገድብን እና ሌላ ስንከፍት ግና መጨረሻ ላይ ታጋቾቹ እኛ እንደምንሆን እናውቅ ነበር፡፡ ያንን የሚያረጋግጥ ተደጋጋሚ የደህንነቶች ክትትል እና ምልክቶች ስለደረሱን መታሰራችን ማስደንገጡ ባይቀርም ያልተጠበቀ ግን አልነበረም፡፡
እስሩ በክትትሉ የተገኘነውን ስድስት የዞን ዘጠኝ አባላት እና ሦስት ጋዜጠኛ ጓደኞቻችንን መሆኑን በተለይ የጋዜጠኞቹ [ቢያንስ ለእኛ] ያልተጠበቀ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ የኋላ ኋላ ስንመለከተው ግን በእኛ አስታኮ እነሱንም ማሰሩ የታሰበበት ዘመቻ እንደሆነ መገመት አይከብድም፡፡ እኛን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሒደትም ቢሆን በቅጡ የታሰበበት ነበር ሁላችንም (ከአስማማው በቀር) ከቀኑ በ11፡00 ገደማ በያለንበት ስንያዝ አስማማው በማግሥቱ ታስሯል፡፡ ሌሎቻችን ቤታችን በሚፈተሸበት ሰዓት ሕጉ የሚፈቅድበት ሰዓት(12፡00) አልፎ ነበር፡፡ በቁጥጥር ስር ካዋሉን በኋላ የሕገ-ወጥ አያያዝ ሰለባ የመሆናችን ሂደት የሚጀምረው ከዚህ ነው፡፡

ማዕከላዊን በክፉ ስሙ ቀድሞ ለሚያውቀው ሰው ግቢውን መርገጥ በራሱ ልብን ያርዳል፡፡ ሆኖም በልቤ /ጓደኞቼም እንደእኔ ሳይሰማቸው አይቀርም/ አንደኛ እኛ ጸሐፊ እንጂ ወታደር ወይም ሰላይ ባለመሆናች፣ ሁለተኛ መቼም ከበፊቱ የተሻለ ሰብዓዊ አያያዝ ሳይኖርም አይቀርም የሚል የዋህ ተስፋ በማሳደሬ ብዙም አልተሸበርኩም ነበር፡፡ የገባሁ እለት ከታሳሪዎች በተሰጠኝ ማብራሪያ ‹‹ሳይቤሪያ›› መግባቴን አወቅኩ፡፡ ከዚያ የ HRW-They want confession የተሰኘ ሪፖርት ላይ የተፃፉ ነገሮች ሁሉ ትክክል መሆናቸውን ለመረዳት የፈጀብኝ ከአንድ ሳምንት ያነሰ ጊዜ ነበር፡፡

ምርመራ ማዕከላዊ ስታይል
ምርመራ በማዕከላዊ ከብልጠት ይልቅ ጉልበት ይበዛበታል፡፡ መርማሪዎቹ የምርመራ ችሎታቸው ተጠርጣሪውን የተጠረጠረበትን ጉዳይ ከማውጣጣት ይልቅ የምርመራ ችሎታ እንዳላቸው ለማሳመን የሚጥሩበት ጊዜ ይበዛል፡፡ ይህም አልሰራ ሲል ጥፊ፣ ካልቾ፣ ከአቅም በላይ ስፖርት ማሰራት እና ግርፋት ድረስ ይዘልቃሉ፡፡ ይህ እንግዲህ እኔ ላይ ከተፈራረቁብኝ አምስት መርማሪዎች እና ሌሎችም አብሮ ታሳሪዎቼ ከነገሩኝ የተረዳሁት ነው፡፡ እርግጥ ሌሎች ‹‹እርቃንን ቁጭ ብድግ›› የሰሩ ተጠርጣሪዎችም ገጥመውኛል፡፡ ከባባድ ቅጣት (ወፌ ላላ ግርፋት፣ ጥፍር መንቀል) የደረሰባቸው ሌሎች ታሳሪዎች አብረውኝ የታሰሩ ቢሆንም ይህ የተፈፀመባቸው ግን ወደማዕከላዊ ከመምጣታቸው በፊት ነው፡፡ ከነዚህ መካከል የሀሮማያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ይገኙበታል፡፡ የሚገርመው በዚህ ዓይነቱ ምርመራ የሰጡት ቃል ለማመሳከርያ ማዕከላዊ መምጣቱ ነው፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ወደማዕከላዊ ከመዛወራቸው በፊት ከባድ ቅጣት የተቀጡበትን ቦታ የት እንደሆነ እንዳያውቁ አይናቸው ተሸፍኖ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ እሥረኞችም መኖራቸው ነው – የደርግን ‹‹ቤርሙዳ›› ያስታውሳል!

እናም በሚያዋርድ እና ክብርን በሚነካ ስድብ በሚያስፈራ የቤቱ (የማዕከላዊ) ጥላ እና ኃይል በተቀላቀለበት የምርመራ ሂደት የተከሳሽ ቃላችንን ሰጠን፡፡ ቃላችን መቶ በመቶ እውነት አልነበረም፡፡ ጫናው በበረታ ቁጥር መስማት የሚፈልጉትን ‹‹ዓመፅ ለመቀስቀስ ፈልገን›› የመሳሰሉ በራስ ላይ ፈራጅ (Self-incriminating) ሐረጎችን እየተናገርን ነበር፡፡ ያም ግን ለመርማሪዎቻችን በቂ አልነበረም፡፡ ስለዚህ በሚጽፉበት ሰዓት እያንዳንዷን ‹‹ሠራን›› ያልነውን ሁሉ ሊያስከስሰን በሚችልበት ሁኔታ እየገለበጡ እና እየበጠበጡ ፃፉት፡፡ አንዳንዶቻችን እየተከራከርን ሲያቅተን ፍርድ ቤት ይፍታው ብለን ፈረምን፣ቀሪዎቻችን የቻልነውን ያህል ተደብድበንበት ፈረምን፡፡ ‹‹ከተናገርኩት ቃል ውጪ አንድም ቃል አልፈርምም›› በሚል እስከመጨረሻው ታግሎ የተሳካለት አቤል ብቻ ነበር፡፡

በምርመራው ሂደት የተረዳነው ነገር ቢኖር የማዕከላዊ መርማሪዎች ብቃት (Intelligence) አርጩሜ ብቻ መሆኑን ነው፡፡ እኔ ምርመራ ሲባል ይመስለኝ የነበረው ፖሊሶች ተጠርጣሪዎችን ፈፀሙ ስለሚባለው ነገር በቂ መረጃ ይዘው ግፋ ቢል ለምንና እንዴት እንደፈፀሙት ማውጣጣት ነበር፡፡ ‹‹ዕድሜ ለማዕከላዊ›› የተረዳሁት ነገር ቢኖር ምርመራ ማለት ለካስ ‹‹የሠራኸው ወንጀል ምንድን ነው?አውጣት!›› ማለት ኖሯል- ማዕከላዊ ስታይል፡፡ ‹‹ነጻ ነኝ›› ቢሉ ሰሚ የለም፡፡ አንዴ ታስረሃል ወንጀል ሊገኝብህ የግድ ነው፤ ካልሆነ ይጋገርብሃል፡፡
አሁን ሳስበው ማዕከላዊ ፈርሶ በሥር-ነቀል ለውጥ እንደገና መቋቋም ያለበት ተቋም ነው፤ ቢያንስ በሁለት ምክንያት፡፡ አንደኛ የምርመራው ሂደት (በራሳችን ጉዳይ እንደተረዳሁት) ትዕዛዝ አስፈፃሚነት ይስተዋልበታል፡፡ ማለትም በመርህ የሚመራ አይደለም፡፡ ሁለተኛ ምርመራው እውቀት መር አይደለም፡፡ ይህ ደግሞ የአገሪቱን ደህንት አደጋ ውስጥ የሚጥል ጉዳይ በምርመራው ድክመት ሳይታወቅ ሊታለፍ ይችላል፡፡ ይህ ችግር የተከሰተው ደግሞ መርማሪ ፖሊሶቹ ከብቃት ይልቅ ለታዛዥነት የተመቹ ታማኞች ሆነው በመመልመላቸው ነው፡፡

‹‹ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ››
በምርመራው ሂደት የተጨቀጨቅነውም ሆነ ተገድደን የፈረምነው ጽሑፎቻችንን የበይነ መረብ ዘመቻዎቻችንን፣ የወሰድናቸው ስልጠናዎችም ሆኑ አንዳንዶቻችን የሰጠናቸው ስልጠናዎች አመፅ ለማስነሳት መሆኑን ‹‹እመኑ›› በሚል ስለነበር የጠበቅነው ግፋ ቢል በወንጀለኛ መቅጫው አንቀጽ 238 ወይም 257 ሊከሱን አስበው ነው ብለን ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የክስ መዝገቡ ሲመጣ ‹‹ሽብር›› ያውም ከአስራ አምሰት ዓመት እስከ እድሜ ልክ የሚያስቀጣ አንቀጽ 4 መሆኑን ሳውቅ በበኩሌ ሳቄ ነበር የመጣው፡፡

ማስረጃ ተብለው ከክስ መዝገቡ ጋር የተያያዙት በአብዛኛው ጽሑፎቻችን፣ የዘመቻዎቻችን፣ የጋዜጣ መግለጫዎች እና በተለያዩ ሥልጠናዎች ወቅት የተዘጋጁ የሥልጠና መመሪያዎች (Manuals) ናቸው፡፡ ከዚህ በተረፈ ከግንቦት 7 እና ከኦነግ ጋር ያገናኛችኋል የተባልነው በሦስት ‹‹ሰነዶች›› ነው፡፡ አንደኛው ናትናኤል ኢሜይል ውስጥ በጥቅምት 2001 ተልኮለት የተገኘ የግንቦት 7 የዜና መጽሔት ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ገና የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ አዋጁ ሳይወጣ፤ ግንቦት ሰባትም አሸባሪ ከመባሉ በፊት መሆኑ ነው፡፡ ሁለተኛ ሶልያና ቤት ተገኘ ተብሎ እናቷ ‹‹ቤቴ ውስጥ አልተገኘም፣አልፈርምበትም›› ያሉት እና ለግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል ሰራዊት ምልመላ መመዘኛ ሰነድ ነው፡፡ ይህ የሶሊ የዘለቀ አቋም ለሚያውቅ ሙግት አያስፈልገውም፡፡ እኔ እንደውም ትዝ ያለኝ ከመታሰሬ በፊት የትዊተር ፕሮፋይሏ ውስጥ የነበረው ‹‹no for war›› የሚል መፈክር ነው፡፡ ሦስትኛው ደግሞ ማሕሌት ኮምፒውተር ውስጥ የተገኘው የኦነግ ፕሮግራም ነው፡፡ በርግጥ አብረው የተገኙት የሌሎች የኦሮሞ ፓርቲዎች ፕሮግራሞች ማስረጃ ተብለው አለመቅረባቸው መረዳት ብቻ – እሷም ለምን ፕሮግራሙን እንደያዘችው፤ እነሱም ለምን የኦነግን እንደመረጡ ያጋልጣልና የእመኑኝ ሙግት አያስፈልገንም፡፡ በመሰረቱ ሦስቱንም ‹‹ሰነዶች›› መያዝ ከቡድኞቹ ጋር ግንኙነት መመሥረት የሚሰሩትንም መውደድ ማለት አየደለም፡፡ ይህም ለመሪዎቻችን ባይታያቸውም እንኳ ለወገኖቻችን የጠፋቸዋል ብዬ አላስብም፡፡

ሌላውና በአስቂኝለቱ ተወዳዳሪነት የሌለው ውንጀላ ‹‹48 ሺሕ ብር በናትናኤል በኩል ተቀብለው ተከፋፍለዋል›› የሚለው ነው፡፡ ይህ ብር ፤‹‹አሸባሪ›› ከተባሉት ቡድኖች የተወሰደ እንዲመስል በሚያደናግር አገላለጽ የተጻፈ ቢሆንም የክስ መዝገቡ ውስጥ የተያያዘውና ገንዘቡ የመጣበት ደረሰኝ እንደሚያረጋግጠው የተላከው ከARTICLE 19 ነው፡፡ ይህንን ጨምሮ በእስር ላይ ለምትገኝ ጋዜጠኛ ቤተሰቦች መደገፊያ /ለእስረኛይቱም ማበረታቻ/ የተላከ መሆኑን ለመርማሪዎቹ በዝርዝር አስረድተናቸዋል፡፡ ይህንን እያወቁ ውንጀላውን ማኖራቸው እውነትም እኒህ ሰዎች ወንጀለኞች ናቸው ብለው አምነው ሳይሆን ‹‹ከቻልን አደናግረን እናስቀጣቸዋለን (የማይችሉበት ሁኔታ አይታየኝም)፣ካልቻልን ደግሞ በቀጠሮ ጊዜ እንገዛበታለን፣ ነጻ እስኪወጡም ቢሆን በእስር እናቆያቸዋለን›› የሚል ክፉ ምኞት ነው፡፡
befekadu
… ሳታመኻኝ ብላኝ!
አህዩት ከታች አያ ጅቦ ከላይ ሆነው ወራጅ ውሀ እየጠጡ ነበር አሉ፡፡ ነገር ያማረው አህዩትን ‹‹አታደፍርሽብኝ›› ሲላት ነገሩ የገባት አህይትም ‹‹ሳታመኸኝ ብላኝ›› አለችው ይባላል፡፡ የኛም ነገር እንደዚያው ነው፡፡
ፖሊስ ሲይዘን እኛ ላይ ይህ ነው የሚባል የመክሰሻ መረጃ አልነበረውም፤ እንዲያውም ከስማችን በቀር የሚያውቁት ነገር አልነበረም፡፡ ሌላው ቀርቶ ከደህንነቶታቸው በአንዱ ልከንላቸው የነበረውን የጽሑፋችንን ስብስብ እንኳን ሳያነቡት ነበር የያዙን፡፡
አሁንም ማስረጃ ብለው ከክስ መዝገባችን ጋር ያያያዙት ቢያንስ በእኔ ግምት ዘጠና በመቶ የሚሆነው ‹‹ሰነድ›› እኛው ነፃ ያወጣናል ብለን የሰጠናቸው ጽሑፎቻችን ናቸው፡፡ በመርማሪዎቻችን ንግግር ውስጥ እኛ ላይ ወንጀል የማግኘት Desperate ፍላጎት አይተናል፡፡ ምናልባትም እንደገመትነው ቢያንስ እስከ 2007ቱ ምርጫ ድረስ ከማኅበራዊ ሚዲያ ገለል እንድንልላቸው ፈልገዋል፡፡ ከዚህ የተሻለም አማራጭ አልታያቸውም ይሆናል፡፡
በእስካሁኑ ሂደት የማዕከላዊን ለገዢው ፓርቲ ወገንተኝነት በዓይናችን አይተን አረጋግጠናል፡፡ ቀጣዩ ደግሞ የፍትሕ ሥርዓቱን በአደባባይ መፈተሽ ይቀረናል፡፡ ለአሁኑ ግን በቅርቡ እንፈታ ይሆን… የሚል ጥያቄ ‹ሕጋዊ› ሳይሆን መላ ምታዊ አማራጮችን እገምታለሁ፡፡
ኢህአዴግ ወይም የኢህአዴግ መንግሥት የሚያዘው ፖሊስ እኛን በቁጥጥር ሥር ሲያውለን ስለወንጀላችን ማረጋገጫ (ጠበቆች Beyond reasonable doubt) እንደሚሉት ዓይነት ባይኖረውም መቼም የሆነች ስህተት ሳላገኝባቸው አልቀርም በሚል ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ወትሮም የተንቦረቀቀ የሚባለው የፀረ-ሸብርተኝነቱ አዋጅ ውስጥ የሚጥለን ነገር በቀላሉ ማግኘት አልቻሉም፡፡ አለመቻላቸው ግን የተነሱበትን እኛን የመክሰስ ዓላማ አላጠፋውም፡፡ የክስ መዝገቡን ሲያዘጋጁ አንድም የረባ ዐረፍተ ነገር ሳይጽፉ ይዘውን ፍርድ ቤት መቅረባቸው በራሱ አንድም የረባ ጥርጣሬና ማረጋገጫ እንደሌላቸው አመላካች ነው፡፡ ቢሆንም በቅርቡ ይለቁናል የሚል ግምት የለኝም፡፡ ለምን;

1ኛ. ኢህአዴግ በጣም የሚናደድባቸው እና ታሳሪውን በሚያዋርድ መልኩ ካልሆነ በቀር ከማያደርጋቸው ነገሮች ውስጥ አንዱ- አንዴ ያሰረውን ተቺውን ፤ ያውም ብዙ ደጋፊ ያለውን መፍታት ነው፡፡ ኢህአዴግ እንደልጅ እልህ ይጋባል ማለቴ ነው፡፡ (ይህንን ስል የእስራችንን ኢፍትሀዊነት የተመለከቱትን ጩኸቶች መጥላቴ አይደለም፤ ያለ እነርሱ መንፈሳችን አይጠገንም ነበር፡በአደባባይ የምናመሰግንበት ቀን ይመጣል)
2ኛ. መጀመሪያ የተጠራጠሩበት እና ኋላ የዋጧት ጥርጣሬያቸው፤ ማለትም (ምርጫውን ተከትሎ) አመፅ ማስነሳት በሚሉት ጉዳይ ላይ እቅድ እንደሌለን ቢያምኑም እንኳን ምናልባት እምነታቸው ከተሳሳተ Risk መውሰድ አይፈልጉም፡፡ ( መጀመሪያም የቀለም አብዩት ዶክመንተሪ አዝማሚያ ያስታውሷል)
3ኛ. ምንም እንኳን ዓመፅም፤ሽብርም የማስነሳት ፍላጎትም አቅምም፤ እንደሌለን ቢያምኑም የገዥው ፓርቲ ጠንካራ ተቺዎች መሆናችንን ስለሚያውቁ እና ስላልወደዱልን ፍርድ ቤት በምንመላለስበት ረዘም ያለ ጊዜ ባለው እስር ወቅት ቢያንስ የእስርን ምሬት እንድንቀምሳት ይፈልጋሉ፡፡ ቅጣትን ጨርሶ በነፃ መለቀቅ እንደማለት፡፡
4ኛ. ኢህአዴግ መፍረድ አይፈራም፡፡

የሁለት ሀገር ስደተኛው –ጋዜጠኛ። (ሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 10.08.2014 (ሲዊዘርላንድ -ዙሪክ)

እንሆ – በዚህ ዘመን ታሪክን እንደ ከሰል አመድ ባደረገ ጽልመታዊ የወያኔ ሃርነት ትግራይ ዘመን – የአንድነቱ ልዑል የአሉላ ማሾ ከወደ ስሜን የብራና ኮከብ መሪን አሰቀድሞ ብቅ አለ። ይህ ደፋርና ንቁ፤ በራስ የመተማመን መንፈሱ ሙሉዑ የሆነ ዕንቡጥ ስሜቱን ለመግለጽ ያለውን ብቃቱን ብራና ቆሞ የሚመስከርለት ድንቅ ወጣት ጋዜጠኛ አብርሃማ ደስታ ነው። አብርሽ የሥርዬት መንገድ ነው።

የወያኔ ሃርነት ትግራይ በጎሳ የሚዘረዝራቸው በደሎችን ሁሉ እዬመነዘር በግልጽ፤ በተብራሩ፤ ስሜትን በሚፈትሹ፤ አጫጭር ዘገባዎቹ ዘመኑ የፈቀደለትን ታሪክ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ ሲያኮመኩመን የቆዬ ትንታግ ነው። ጋዜጠኛና መምህር አብርሃም ደስታ „ ትግራይ የኢትዮጵያዊነት ባለ ጉልትነቷን እዬፈገፈገ እንድታጣ ከዘመተባት ጠላቷ ከአረሙ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌስቶ ጋር ትፋታ ዘንድ ቆሞ ያሰተማረ – የሰበከ – የመከረ ትጉህ ወጣት ነው።

ታናሼ አብርሽ በፎሎቄማ የአጻጻፍ ለዛው የብዕር ፍቅረኞችን ሰጥ ብሎ እንደሚወርደው ኢትዮጵያዊ ወንዝ መንፈሳቸውን የገዛ፤ ማህል ላይ ወለል እያለ የሚያስቸግረውን ግራጫማ የዞግ ወረርሽኝ በሽታንም ሳይቀር በመግራት ህሊናን ሚዛን ላይ ያሰቀመጠ –  ዬእርቅም ድልድይም ነው። በቀልና እኛ - በበደል ዓይን፤ በቀልና እኛ በፍትህ ጆሮ፤ በቀልና እኛ በመገፋት የዕንባ ምጥ እያቆላመጠ በሥነ – ጥበብ ማራኪያዊ ውበት እንድንፈታተሽ ከህሊና መንበር ጋር ፊት ለፊት ያገናኘ ብቁ የጥበብ ሰው ነው። እንደ እኔ ብዙ ነፍሳትን ከጥፋት ውሃ በሁሉም አቅጣጫ ታድጓል ባይም ነኝ።

አብርሽ በራሱ ውስጥ ስሜቱን – ፍላጎቱን – ራዕዩን አቅርቦ እያባበለ – እያሟገተ ቀልብን ይዞ መልእክቱን በማስተዋል እንከታተለው ዘንድ በብቃቱ ፍቅርና ሰፊ ተደማጭነት ያገኘ ትጉህ የብዕር ገበሬ ነው። አብርሽ ጨርሶ ሚዲያ ዳስሷቸው ያማያውቀውን የገበሬ መንደሮችን ሳይቀር ከትግራይ ወጣ ብሎም የዳሰሰ ወርቅ ወጣት ነው። ለምሳሌ በዘመነ ታሪካቸው ብዕርና ብራና ጎብኝቷቸው የማያውቁትን በጎንደር እንደ „ጮንጮቅ“ ያሉትን እጅግ ትንሽ የገበሬ መንደር ሳይቀር የደረሰውን ህዝባዊ በደል በማጋለጥ ሃቅን አደባባይ አቅርቦ ዬወያኔ ሃርነት ትግራይ የነፃነት ጠላትንትነት፤ የርትህ ዘረፋን፤ የሰላማዊ ሰዎችን ሰላም ቀማኛነትን ቁልጭ ባለ ንጹህ አግባቢ ቋንቋና በውባውብ የቃላት ቅንብሮቹ ዘዬ ዕውነትን ለባለታሪኩ ለፍተሻ ያቀረበ ባተሌ የሰከነ ጋዜጠኛ ነው።

አብርሽ መምህር እንደመሆኑ መሰሉን ለመተካትም በትምህርቱ ዘርፍም አባታዊ ሃላፊነቱን የሚወጣው ወያኔ ሃርነት ትግራይ „ ከትግራይ ውጪ ያሉ ኢትዮጵውያን በጥቅሉ አማራ በሚል ሥያሜ ሰው ያልሆኑ፤ ሁለት ትላልቅ ጆሮ ያላቸው። አንዱን ጆሮውን ለብሰው፤ ሌላውን አንጥፈው የሚተኙ“ እያለ ትግራይን ከኢትዮጵያ ገንጥሎ፤ ጥላቻን ኮልኩሎ በበቀል ብቅል አብቅሎ ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት የነበረውን መሬት ያያዘ የቁርሾ ብክል ደም በማምከን በኢትትዮጵያዊነት መንፈስ የኔ ፍሬዎችን ያጠበ፤ ያጸዳ፤ የወያኔ ቆሻሻውን ሁሉ የጠረገ ብልህ ወጣት ነው። መምህር አብርሃ ደስታ በተማሪዎች የኢትዮጵያዊነትን አቅም በመገንበት፤ ኢትዮጵያዊነትን ብድግ ያደረገ ለጋ ወጣት ነው። እንደ ሌሎቹ የጎሳ ጥመኞች አዛውንት መምህራን የመረጥከውን መውሰድ ትችላልህ በማለት ታሪክን ለባንዳ በረድ ያለጋለጠ ንቁ ወጣትም ነበር። ታሪክን ማህል ላይ ገትሮ ያለጠቆረ የሙያውን ሥነ – ምግባር ክብር ያስጠበቀ ታታሪ ወጣት ነው። ስለሆነም ይህ ጋዜጠኛ፤ ጸሐፊና መምህር ወጣት ድርብ ሃላፊነቱን የተወጣ – የቆረጠ የቀለም – ቀለማም አባትም ነው።

እጅግ የምትናፍቁኝ የሀገሬ ልጆች። „የሥላሴ አንድነትና ልዩነት“ ለተዋህዶ ልጆች የተሰጣቸው አባቶች ብቻ ነው የሚተረጉሙት – የሚያመሳጥሩት። „ካህን“ በመሆን ብቻ ይህ ታላቅ የዕምነት ዶግማ ሊደፈር ከቶውንም አይችልም፤ ስለ „ነገረ ማርያምም“ ቢሆን በተመሳሳይ ሁኔታ የተፈቀደላቸው ብቻ አንደበታው ተከፈቶ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ በአማንያን ሥረ ህሊና ማብቀል ይችላሉ። ታናሼ ጋዜጠኛ አብረሃም ደስታም „ማንነትን“ የተነተነበት መንገዱም ሆነ የሂደቱ ረቂቅነት ፍጹም ልዩ ስለነበር „እኔ ማን ነኝ? ከዬት ተገኘሁ? እንዴትስ መጣሁ? ከማንስ ተፈጠረኩ? ግንደ – ዘሬ እንዴት ተፈጠረ? ቅርንጫፉና ግንዱ እንዴት ሀረግን ፈጠሩ?“ በማለት ልክ የተቋም ያህል ነበር ያስተማረው። ዬአብርሽ ጸጋ ከሩቅ፤ ወይንም ከወንዝ ወዲያ ማዶ ወይንም ህዋው ላይ አይደለም የሚነሳው – ከተጨባጩ ከጠረኑ ከራሱ ውስጥ ተነስቶ አካባቢውን ቃኝቶ ደረጃውን እዬጠበቀ ወደ ብሄራዊ፣ አህጉራዊና፣ ዓለማቀፋዊ ትንፋሹን ያመጠዋል – ያጣጥመዋል። መሬት ይዞ ስለሚነሳ ዘርቶ ሊያበቅል የሚፈልገው ነገር  እጥፍ ድርብ እንደ ተፈጥሮው ማብቀል ዬቻለ ትምህርተ – ገቢራን ነው። አብርሽ ለትግራይ ህዝብ የታሪኩ አባወራ እንደ ሥሙ የአብራሃሙ ቤት ነው። „መድህን“ ቢሉትም ይገባል። ታዳሚዎችም ሆነ አድናቂዎቹ ዕልፍ ነን።

እኔ አብርሽን እጅግ አውደዋለሁ። እሱ በሚጽፋቸው ጹሑፎች ሥር የአስተያዬት ግድፈቶች ከሥር ተጽፈው ሳይ እጅግ ልቤ ይቆስል ነበረ። ይህ ልጅ – ይህ ወጣት – ይህ ቀንበጥ – ይህ ጀግና በወያኔ ሃርነት ትግራይ ሆነ በሰሉ የወያኔ ደጋፊዎቹ  የከረፋ የበደል ክምር ተጠያቂ ሊሆን ከቶውንም ፈጽሞ አይቻልም።

ወገኖቼ ይህን ቢፈቅድ እኮ ጋዜጠኛ አብርሃም ደስታ ለዶተሬትነቱ ሰፊ ዕድል ማግኘት ይችል ነበር። ተነጥፎ ተጎዝጉዞለት። ሀገር ውስጥ እኖራላሁ ቢልም እስከ ሚ/ር ደረጃ የሚያደርስ ዕድሉ ሰፊ ነበር። የመጀመሪያውን የወያኔ ሃርነት ትግራይ መስፈርት የሚያሟላ ጉልህ ወጣት ነበር። ግን አላስፈለገውም። መኖር የፈለገው በእውነተኛው ዓለም በጋህዱ ዓለም ነበር። ገሃዱ ዓለም የሚፈልገው ደግሞ እንደ ተፈጥሮው የሆነ ነፃነትን ነው።

የመኖር – የመተንፈስ፤  የመናገር፤ የመጻፍ፤ የመደራጀት፤ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ፤ የህግ የበላይነት፤ በድምጽ የሚመራ ሀገር፤ በደል – አድሎ – ስጋት – ረሃብ የሌለበት የእኩልነት ዜግነት ዓለም ነው። ይህን ከወያኔ ሃርነት ትግራይ የ40 አመት ትግል ጠብቆ ማዬት አልቻለም። ስለዚህ ከበደሉ ማሳ እራሱን አውጥቶ እሱ ስለሚያልማት ኢትዮጵያ መናገር ጀመረ …. ማስተማር ጀመረ …. መስዋዕትነቱን ተርጉሙት በነፃነት ህገ – ህግጋት መገዛት ቻሉ! በማለት ወቀሳውን ካለይሉኝታ  ለአራዊቱ ወያኔ  ገለጸ …. ሰሚ አጣ … እንዲያውም ተጠቂም ሆነ።

እኔ በጣም ለረጅም ጊዜ አስተውለው የነበረው አብይ ጉዳይ „ጋዜጠኛ አብርሃ ደስታ“ ለማለት እንኳን ጋዳ ነበር። ሙያው የሚጠይቀውን ያሟላ ሆኖ እያለ። ዘገባዎቹ ትኩስ – ግልጽ – የተብራሩ – ከማህበረሰቡ የተነሱ – ፈጽሞ በግነት ያልተወረሩ – ብዙኃኑን ያደመጡ –  አጭር – ደፍረው ጦርነት ውስጥ የሚያገቡ – ቅራኔ የተጋሩ፤  ዬእውነትን ጅረትን ተከትው ዬሚጓዙ – የዘመኑን ባህሪ ያደመጡ ነበሩ። ይህ ሙያው የሚጠይቀው በጋዜጠኛ አብርሃም ደስታ በቀጥታ በተፈጥሮው ያገኘው ልዩ ብቃቱ ነበር። ለነገሩ በሥልጠና የሚገኝ ክህሎት ነበር — ግን እሱ ከላይኛው ተፈቀደለት።

ወደ ሥነ -ጹሑፍ ሥልጡነነቱ ስትሄዱ ደግሞ  የነጠረ አቅም ነበረው፤ ጹሑፎቹ  የወያኔን ሆድዕቃ አሳምረው ጎርጉረው ግን ሳይጠገቡ እንዳጓጉ ላጥ ይሉ ነበር። ልብን እንደ ቅል አንጠልጥለው። ዝንፈት ያልጎበኛቸውም ነበሩ።

በሰብዕዊ መብት ተቆርቋሪነቱም ቢሆን ቁስሉ የተሰማው መንፈስ ነበር የሚታይበት። በሴቶች የእኩልነት ተሳትፎ ላይም አንጋፋ – ጎልማሳ – ወጣት – ጋዜጠኞች የሚዘሉትን ሥነ – ምግባር ያሟላ ነበር ማለት እችላለሁ። እጅግ አብዝቼ እምከታተለው ዘርፍ ነውና። በአብርሽ የዜና ትንተና የመረጃ አቅጣጫ ደግሞ ድንቅ ትርጉም ይታፈሳል። ዘገባዎቹ ሁሉ – ከቆዳ መልስ ነክቷቸው አያውቅም።  ወይንም ተቆርጦ እንደ አደረ ዝንጣፊ ጥንዙል አልነበሩም። ትኩስ ትኩሱን ለመንፈሳችን ይቀልብን ነበር። እንሆ አሁን ትግራይ አንደበቱ ተዘጋ …. ስለ አሉላ መንፈስ፣ ስለ አሉላ ጸሐይ – ትግራይ ምን ይል ይሆን? ጸጥ – ረጭ – ዝም —-  ያቺ የእኔ ጀግና ወ/ሮ አልጋነሽ ገብሩና መንገድ እንደወጡ ያዳመጥነው ዬፍሬዎቻስ – የነገ ተስፋዎቻችን ጉዳይ ማን ይንገርን – ዝግት ድርግም ያለ ጉድ …. ዳፍንት!

እኔ አንጀቴን የሚበላኝ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ጎጣዊ ማንፌስቶ ትሸታላቸሁ ብሎ የሚመጣን ኢትዮጵያዊ ዜጋን ለመቀበል ያለን አቅም ስስ መሆኑ ነው። ሁልጊዜ ጥርጣሬ። ሁልጊዜ ወቀሳ። ሁልጊዜ ዱላ። አብሶ ወጣቶች ባልበሉት ዕዳ ስለምን እንደሚወቀሱ ፈጽሞ አይገባኝም። እንዲገባኝም አልፈቅድለትም።

ማያያያዣ ነገር – አሁን የአንድነቱ አንደበቱን – ብቃቱን – አቅሙን ሳልጠግበው ለካቴና የበቃው አቶ ሃብታሙ አያሌው „ዬወያኔ ደጋፊ ዬነበር“ በሚል ከልብ ለመቀበል የነበረን ፈቃደኝነት ያረረ ነበር። አሁን ሲታሰር ጀግና እንለዋለን? ወያኔ አሁን ከሚያደርስባቸው ማናቸውም ስቃይ የኛውም የመንፈስ ረገጣ ሆነ ጥቅጠቃ ዘመን ይቅር የሚለው አይመስለኝም። አንድ ሰው በነፃነት ትግሉ እሰለፋለሁ ሲል በጣም ብዙ ነገሩን ነው የሚያጣው። የሚተርፈው የመንፈስ ጥሪት ለህሊና ማደሩ ብቻ እንጂ በግራ በቀኝ በሚወርደው ወጀብ ያለው ወጨፎ መመዘን ከቶ አይቻልም።

ለነፃነት ታጋዮቻችን ለመንፈሳቸው ጥበቃ ጥንቃቄ በሚመለከት ምድረበዳ ነው። ወያኔ እዬከፈለ። ውጭ ሀገር ላሉ ቱቦዎቹ ሳይቀር እንኳን ቀለብ እዬሰፈረ የእኛ ደግሞ በብላሽ ለማገልግልም ቆመጥ —- እም!

እርግጥ ተሰውረው – ተቀላቅለው አንድ ደረጃ ላይ የሚሾልኩ ይኖራሉ። ከዚህ ስጋት አንጻር ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አራሳቸው ከፈለጉ ወደ ውርዴታቸው ያዝግሙ። በእኛ በኩል ያለውን መልካም አቀባባልና ፍቅር ከመሰጠት መቆጠቡ ግን የማይጠቅም ነው። ባይሆን ደረጃውን ይጠብቅ ያግባባል — እንጂ ገና በሩ ሳይደርሱ …

አንጀቴን እዬበለኝ የምጽፈው አብርሽ የሁለት ሀገር ስደተኛ የነበረ መሆኑ ነው። እኛ የነጻነት ፈላጊ ቤተሰቦች በይደር ዬያዝናቸው ጉዳዮች ነበሩን። ወያኔ ከጎጥ ዶክተሬኑ በማምለጡ እርምጃውን እዬተከታተለ መተንፈሻውን መዝጋቱ በሁለት ወጀብ ሲንገላታ እነሆ በእጅ ወድቆ እንደፈለጉት ይዘለዘላል። የበለጠ – የቀደመ – የተሸላ በመሆኑ ብቻ ሳይሆን „የኢትዮጵያዊነት ፋና“ በመሆኑም ጭምር ሁለመናውን ይደምስሱታል።

ፎቶዎቹን ስብስብ አድርጌ ስመለከታች መልሼ በዚህ መንፈስ እንደማለገኘው ሳስበው መንፈሴ ይመረቅዛል – በመግል። ፈዞ በድኑን ብቻ ይሆናል ዬሚሰጡን። ቀጣዩ የእሱ የወደፊት ተስፋ ሁለት ያጣ ጎመን እንዳይሆን እንደማንንኛውም የብዕር አርበኛ ለዓለም ዓቀፉ የብዕር ሽልማት ይበቃ ዘንድ ተግቶ መሥራት ያስፈልጋል። የታሪኩ ጠበቂና ዘብ አደር ልሆንለት ይገባል። አብሶ ወጣት ኢትዮጵውያን አብርሽን እንደ ወጣት አብነታቸው፤ እንደ ወጣት ሙሴያቸው ሊያዩት እንደሚገባ በእናትነቴ ዝቅ ብዬ እጠይቃለሁ።

የተግባር ዲታው እውነተኛውና አንጋፋው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበርም በክህሎት የተቀመመውን ተመክሮውን አበልጽጎ ለሙያ አጋሩ ያለውን አክብሮትና አድናቆት ሊገልጽ ዬሚችልበትን ስልት መፍጠር እንዳለበት አሳስባለሁ – በትህትና። በአንድ ወቅት የክፍለሃገር አዳራጃችሁ ነበርኩና – ህገ ደንባችሁ እንዲህ ለሙያው አርበኛ አክብሮቱን እንደማይነፍገውም አስባለሁ። በተጨማሪም ጋዜጠኛና መምህር ርዕዮት ዓለሙም ታሪካችሁ ናት። እሷንም አዘውትራችሁ ልታስቧት እንደሚገባ በትህትና እጠቁማለሁ።

በሌላ በኩል ደግሞ እንደ ሥነ ጥበብ ቤተሰብ አባልንቴ ወጣት ከያንያን አብርሽን – ክታባቸው እንዲያደርጉት በትህትና አሳስባለሁ። እንደ ጋዜጠኝነቴም ደግሞ የሙያ አጋራቹ ከፊተኛው ረድፍ ላይ በመገኘት ለሙያው አህጉርና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ወቅታዊ መረጃዎችን በመላክ – ተግባሩን በማስተዋወቅ እረገድ ተጓዳኝ ተግባራትን አቅሙ ያላችሁ ወገኖቼ ትከውኑ ዘንድ በአጽህኖት አሳስባለሁ።

ምን ቀረኝ? ለሰብዕዊ መብት አስከባሪ ድርጅቶችም መረጃዎችን በአጫጭር በእንግሊዘኛ ከተሰሩ ባለው መስመርና ግንኙነት የሎቢውን ተግባር በቀላሉ መከወን ይቻላል። አብሶ የፍርዱን ሂደት የቀጠሮ ቀናቱን ውሎዎች ሁሉንም በእንግሊዘኛ መሠራታቸው እጅግ ጠቃሚው መንገድ በመሆኑ አትኩሮት ቢሰጠው መልካም ነው።

ማህበራዊ ድህረ ገጾች፤ የመወያያ መድረኮች፤ ሚዲያዎች ለአጋራቸው – ለጀግናቸው የነበራቸው አቅርቦትና አክብሮት አብነት ነበር ማለት እችላለሁ። የአብርሽ ጹሑፎች ሆኑ ዘገባዎችን በሽሚያ ነበር የሚያወጡትና አዬር ላይ የተገባውን አክብሮት ይሰጡት የነበረው። ተመስገን። በዚህ ልጽናና።

በቀጣይም በአብርሽ የነጻነት ራህብተኛ ጹሑፎቹ ዙሪያ ውይይቶች – ትናንሽ ወርክ ሾፖችን በዬአካባቢው ፈጥሮ አጀንዳ ማደረግ የተገባ ይመስለኛል። አሁን ለምሳሌ „እኔና ሚኒሊክ“ የሚደንቅ ጹሑፍ እኮ ነው።  ስለሆነም የቆዩትንም  ከአርኬቡ እያወጡ ድጋሚ እንዲነበቡ ቤተኛ ማደረጉ መንፈሱ ከመንፈሳችን ጋር እንዲቆራኝ ይረዳል። አብሶ አሁን ፆም ስለሆነ በጸሎት መተጋጋዙም መልካም ነው። ፎቶውን በፌስ ቡኮች – በቲተር አካውንቶች ሁሉ መጠቀም ሌላው መንፈስ አራሽ መንገዶቻችን ሊሆኑ ይገባል። ጹሑፎቹ የማሰባሰብና ታሪካዊ ቋት ማበጀትም – ነገን ያሳድራል።

በማናቸውም ብሄራዊ ህዝባዊ ስበሰባዎች ሰላማዊ ሰልፎች፤  ጀግናችን አጀንዳችን፤ ጀግናችን ኮከባችን መሆኑን ከውስጣችን ሆነንበት እንታይበት ዘንድ ዝቅ ብዬ አሳስባለሁ። ለእኔ አብርሽ የአንድነቱ ልዑል ዬአሉላ አባነጋ የአደራ ማሾዬ ነው። በብዙ ጹሑፎቼ እሱን እንደ ማመሳካሪ እያደረኩኝ ሰርቼበታለሁ። አሁንም ከልቤ ውስጥ ትንሽ ሙዳያ አለች። በእሱ ውስጥ ታናሼ የሙያ አጋሬ፤ የሥነ ጥበብ ቤተኛዬ፤ እንዲሁም የነፃነት ፈላጊ ቤተሰቤ አበርሽ በክብር ለዘለአለም ይኖራል፡“ አራዊቶች የፈለገውን ነገር አስገድደው ያሰፈርሙት። የእሱ ነው ብለው ይጻፉ። ለእኛ የባንዳ መረጃ ምናችንም ነው። ይልቁንስ አብርሽን የሚገልጸው የሚያብራራው ዬሚያነበው “ የኢትዮጵያዊነት ህግ – አመክንዮ“ መሆኑ ብቻ ነው መስተውታችን ሆነ ሰነዳችን።

ማንም ሰው የአብርሽን ፍቅር ሊቀማን አይችልም። አይፈቀድም። የተከለከለ መንገድ ነው። የእሱ የተስፋ ማሳዎች ዕሸቶች ናቸው – ነገን ያበልጋሉ። እኔ አብዝቼ  እወደዋለሁ። የእሱ መፈጠረ ከብዙ ነገር ታድጎናል። ኢትዮጵያን ከበቀል ያዳና ትንሽዬ ወጣት የድህነት መንገድ ነው …..  አብርሃ ደስታ። አጋጣሚና ሁነኛ ጊዜ አግኝቶ ቢሆን ኖሮ ሰፊ ማሳን ማልማት በቻለ ነበር። ታዲያ ወ ያኔ አቅል ብሎ አልሰራለት። ፈሪ – ብዕርን መድፈር የተሳነው ልፍስፍስ።

የትግራይ ህዝብ ቢያውቀው አብርሽ እንደ መጥምቁ የኋንስ „መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኃ ግብ“ እያለ እንደ መራው ሐዋራያዊ ተግባር ነው የፈጸመው እሱ እራሱ መልእክተ የኋንስ ነው። በሁሉም ዘርፍ ሲመዘን የአብርሽ ተልዕኮ የብዙኃኑ ፍቅርና ሰላም የተራቆተው ወያኔ ሃርነት ትግራይ እርቃነ – መንፈስ ጎጂ ጉዞ ስለመሆኑ፤ ነገን የማያሳድር ዛሬንም ያማያበርክት ስለመሆኑ ነበር እንደ ተሰጠው መክሊት ሲፈጽም የቆዬው።

ክወና – አብርሽ ሞገድ ነው – ሃቅን የታጠቀ፤ አብርሽ ነበልባል ነው – በራስ መተማመንን የዋጠ፤ አብርሽ ፍቅር ነው  የነፃነት መርህን ከልቡ የተቀበለ። አብርሽ አብነት ነው መከራን ለመቀበል የፈቀደ። ስለሆነም ስቃዩ ስቃያችን፤ መከራው መካራችን፤ ሰቆቃው ሰቆቃችን ነው። የኔ አባት ላደርክልን መልካም ነገር ሁሉ አመስግንሃለሁ። ውድድድ /////

 

የኔዎቹ እንሰነባበት – ፍቅርም – ናፍቆትም – ውስጥም ተሸለማችሁ። ቸር አገኛችሁ ዘንድም አምላኬን ጠዬኩኝ። ደህና ሰንብቱልኝ። ውድድድ

 

ጀግኖቻችን የመንፈስ ሀብሎቻችን ናቸው!

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር!

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

Comment

የከዱ የግንቦት 7 አባላት አቶ አንዳርጋቸውን እያሰቃዩ ነው ተባለ፤ * 2 መምህራንና 1 ዳኛ በአንዳርጋቸው ጉዳይ ታፍነዋል

$
0
0

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን መያዝ ተከትሎ ለወያኔዎች ከአዲስ አበባ እስከ ደብረዘይት ትልቁን የምርመራ ስራ እየሸፈኑ ያሉት ከግንቦት ሰባት ሕዝባዊ ሃይል ጋር በኤርትራ የነበሩ እና ከአቶ አንዳርጋቸው ጋር የፖለቲካ ስራ ሲሰሩ የነበሩ በኋላም ከድተው የገቡ ቅጥረኞች መሆናቸው ታውቋል። እነዚህ ቅጥረኞች ከመጀመሪያው ሰርጎ ገቦች እንደሆኑ ሳይጠረጠር ወደ ግንቦት ሰባት ከገቡ በኋላ ከአቶ አንዳርጋቸው መያዝ ቀደም ብሎ በመክዳት ወደ ወያኔ የተቀላቀሉ ናቸው ሲል ጦማሪ ምኒልክ ሳልሳዊ ዘገበ።

Andargachew Tsigeእንደ ምኒልክ ዘገባ ከሆነ በአዲስ አበባ እና በደብረዘይት ትልልቅ ሆቴሎች ተይዞላቸው በምርጥ መኪኖች እየተንሸራሸሩ አቶ አንዳርጋቸውን በማሰቃያ ክፍል ውስጥ በማምጣት እውነቱን አውጣ አንተ እንደዚህ ብለኸን አልነበረም በማለት በተለያየ ጊዜ በስብሰባ እና በውይይት ወቅት የተነጋገሩትን የፖለቲካ ኦፕሬሽኖችን እና የትግል ስትራቴጂዎችን በመጥቀስ ከፍተኛ ስቃይ እና ድብደባ እያደረሱብት ነው።

ከሕወሃት ከአንድ ብሄር ከተመለመሉ መርማሪዎች ጋር በጋራ በምርመራ ላይ የተሰማሩት ሶስቱ የግንቦት ሰባት ከሃዲ አባላት አንዳርጋቸውን በማሰቃየት ላይ ያሉት -
1) ሽታው ሽፈራው ኤርትራ የነበረ የጎጃም ሰው
2) ቴዎድሮስ ስዩም ኤርትራ የነበረ ከአዲስ አበባ የሄደ
3) ኢልያስ ጥረት ጎንደር ውስጥ የነበረ እና ከአንዳርጋቸው ጋር ሲሰራ የነበረ ናቸው ሲል በዝርዝር የጠቆመው ጦማሪ ምኒልክ ሳልሳዊ በወያኔ ተንኮል ተተብትበው ግንቦት ሰባትን በመክዳት ለምቾታቸው የሕዝብን ትግል በጥቅም በመለወጥ በዘመናዊ መኪና እየተንፈላሰሱ በአዲስ አበባ እና ደብረዘይት ምርጥ ሆቴሎች ውስጥ እየተዝናኑ የነጻነት ታጋይ የሆነውን አንዳርጋቸውን በቶርች በማሰቃየት ላይ መሆናቸውን ዘግቧል።

ምርመርውን በመሪነት የሚያንቀሳቅሱት የሕወሓት ደህንነቶች የሆኑ የትግራይ ተወላጆች ሲሆኑ በአከባቤው አንዳርጋቸውን በተመለከተ ለብአዴን ይሁን ለ ኦሕዴድ ሰዎች ምንም አይነት መረጃ እንዳይሰጣቸውና ወደ ማሰቃያ ክፍሉ ምንም እንዳይቀርቡ ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገ እንደሆነ ለማረጋገጥ መቻሉን የገለጸው ጦማሪው ከአንዳርጋቸው ጋር የተያያዘውን የሃገር ውስጥ ኔትወርክ በማፈራረስ ረገድ ከላይ ስማቸው የተጠቀሰው ከሃዲዎች እስከ ክፍለሃገር ድረስ በስፋት እየሰሩ ሲሆን እስካሁን በማፈራረስ ሙከራው ምንም አይነት ውጤት እንዳልገኙ ታውቋል ብሏል።

ጦማሪው ዘገባውን ሲቋጭም “ከአንዳርጋቸው ጋር በተያያዘ ከየክልሉ የግንቦት ሰባት መዋቅር ውስጥ አሉ የተባሉ እየተለቀሙ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ከጎንደር ክፍለሃገር መምህር ተስፋዬ ተፈሪ እና መምህር ጌታቸው የተባሉ የሁለተኛ ደረጃ መምህራን እንዲሁም የጎንደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ እንደሆነ የሚነግረው አቶ አበራ በከሃዲዎች ጥቆማ ከሃምሌ አጋማሽ ጀምሮ ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ የት እንደታሰሩ እንኳን እንደማይታወቅ ተገልጿል።” ብሏል።

ለዲያስፖራ ኗሪ ኢትዮጵያውያን በሙሉ።

$
0
0

endaleየትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ)ለስድብና ለማዋረድ ሥራ በክፍያ ያሰማራቸው ቅጥረኛ ባንዳዎችን እንዋጋ!! ለሃገርና ለሕዝብ የቆሙ ግለሰብ ኢትዮጵያውያንን፤ ድርጅትና፤ ተቋማትን እያሳደዱ እንዲሰድቡና እንዲያዋርዱ ወያኔ አሰልጥኖ ያሰማራቸው ቅጥረኞች ሕዝብን ስይፈሩና ሳያፍሩ የባንዳነት ተግባራቸውን ቀጥለውበት ይገኛሉ። የኢትዮጵያ መንግሥት የሚል ስያሜን የያዘው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ወያኔ) እነዚህን ተሳዳቢ ቅጥረኞች ያሰማራው የቻይና መንግሥት የኮሚንስት ፓርቲውን አመራር የሚቃወሙና የሚተቹ ግለሰብና ተቋማትን ለማሸማቀቅ ሲል አቋቁሞት የነበረውን የ50 ሳንቲም ፓርቲ (50 Pence Party ) ዘዴን በመውረስ ሲሆን ዓላማውም ለወያኔ የማይመችን ኢትዮጵያዊ ግለሰብ፤ ማህበረሰብንና ተቋምን ሁሉ በመስደብ በማዋረድና በሃሰት ክስ በማሸማቀቅ ቅስሙን ሰብሮ ተገዢ ለማድረግ ነው። —- [ሙሉውንለማንበብእዚህላይይጫኑ]—-

Hiber Radio: የአንድነትና መኢአድን ውህደት ያገዱት የወ/ሮ አዜብ ወንድም መሆናቸው ተገለጸ፤ ከደ/ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ስደተኞች የጉበት በሽታ እያስተላለፉ ነው

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ ነሐሴ 4 ቀን 2006 ፕሮግራም

>

አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ ለህብር ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)

<...>

አቶ ኦባንግ ሜቶ አሜሪካ የኢትዮጵያን አምባገነኖችን በመጋበዙዋ የቀረበው ጠንካራ ተቃውሞ ውጤታማ መሆኑን ለህብር በሰጡት ቃለ መጠይቅ ገለጹ (ሙሉውን ያዳምጡት)

የአሜሪካና የቻይና የኢኮኖሚና የዲፕሎማሲ ግብ ግብ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በተንሰራፋባት አፍሪካ ሜዳ ላይ (ልዩ ዘገባ)

ኢራቅ የተወለዱት አዲሶቹ አሸባሪዎችና በክርስትና ሀይማኖት ተከታይ ላይ ጭምር የፈጸሙት ጅምላ ግድያ እና የመስፋፋታቸው ስጋት (ልዩ ጥንቅር)

የኢትዮጵያዊነት ቀን ክብረ በዓል ዝግጅት በቬጋስ(ቃለ መጠይቅ)

ሌሎችም አሉ

ዜናዎቻችን

* የአንድነትና መኢአድን ውህደት በህገወጥ ውሳኔ ያገዱት የምርጫ ቦርድ ባለስልጣን የወ/ሮ አዜብ መስፍን ወንድም መሆናቸው ተገለጸ

* መኢአድ የቦርዱን ውሳኔ ሳይቀበል የስራ ማቆም አድማን ጨምሮ ጠንካራ ተቃውሞ እጠራለሁ አለ

* የእንግሊዝ መንግስት በአቶ አንዳርጋቸው ጉዳይ የኢትዮጵያውን አገዛዝ ባለስልጣናት ጠርቶ አነጋገረ

* ኢ/ር ግዛቸው ገዢው ፓርቲ በምርጫ ቦርድ በኩል የተቃወመውን የአንድነትና መኢአድ ውህደት የሚያቋርጥ ውሳኔ በችኮላ ማስወሰናቸው ግራ መጋባት ፈጠረ

* 24 ኢትዮጵአውያን ስደተኞች ሰሞኑን ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በህገ ወጥ መንገድ ገባችሁ ተብለው ተያዙ

* ከደ/ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ስደተኞች የጉበት በሽታ ለኢትዮጵያውያን እያስተላለፉ መሆኑ ተገለጸ

* ኢትዮጵያዊው የድህረ ገጽ ባለቤት በሕወሓት አገዛዝ ላይ የ120 ሚሊዮን ዶላር ክስ ከፈተ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ


ታሪክ ሲደገም! –ከኢየሩሳሌም አረአያ

$
0
0

Interview with the former Ethiopian PM Fikre Selassie Wegderes – Pt 1
የደርግ ዋና ሞተር የነበረው ፍቅረስላሴ ወግደርስን ጨምሮ በርካታ ነፍሰ በላዎች ከእስር ተፈተው መፅሐፍ በነፃነት ሲፅፉ እያየን ነው። ለምን ፃፉ የሚል ተቃውሞ የለኝም። ነገር ግን ፍቅረስላሴ ደራሲ በአሉ ግርማን ቀርጥፈው ከበሉ ቁልፍ የደርግ ባለስልጣናት ዋናው ሆኖ ሳለ አንድም ነገር ስለበዓሉ ግድያም ሆነ ስለጨፈጨፏቸው በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ምንም ያለው ነገር የለም።

እንዳውም ደርግ ትክክለኛ እንደነበረ ሊሰብክ ሞክሮዋል። የጥቃቱ ሰለባዎች ምን እንደሚሰማቸው ለማወቅ የግድ እነሱን መሆን አይጠበቅም። እነፍቅረስላሴ ወንጀላቸውን ሸፍነው ውሸት እየፃፉ በሚኖሩባት አገር እውነት የፃፉ ሰላማዊ የአገር ልጆች ዞን 9ኝና ጋዜጠኞች፣ የተቃዋሚ አባላት እነሃብታሙና አብርሃ የመሳሰሉት በሚያሳዝን ሁኔታ በነፍቅረስላሴ ቦታ ወንጀል ተፈብርኮባቸው እስር ቤት መግባታቸው ያቃጥላል።

እነፍቅረስላሴ በበአሉ ግርማ ላይ ያነሱትን የጭካኔ በትር የአሁኑ ገዢዎች ከላይ በጠቀስኳቸውና በነእስክንድርና ርእዮት ወዘተ..ንፁሃን ላይ በተመሳሳይ የጥፋት ሰይፋቸውን መዘዋል። የደርግ ጨካኞች እነገስግስ ገ/መስቀልና እርገጤ መድበው በተባሉ ይፈፅሙ የነበረውን ዘግናኝ ስቃዮች “እቃወማለሁ፣ ታግየዋለሁ” ይል የነበረ ድርጅት ወይም ስርዓት ዛሬ እነ ታደሰ መሰረትን የመሰሉ ገራፊዎች አሰማርቶ ንፁሃን የኢትዮጵያ ልጆችን እየገረፈ ማሰቃየቱ ታሪክ እራሱን እየደገመ እንዳለ በቂ ማሳያ ነው! ገዢዎቹ ግን ማወቅ ያለባቸው ነገር እስር፣ ግርፋትና ስቃይ በጭራሽ መፍትሄ ሊሆኑ አይችሉም። ደግሞም በግዜ ሒደት እናንተና የደርግ ነፍሰ በላዎቹ እነፍቅረስላሴና ተከታዮቹ በፍርድ አደባባይ መገተራችሁ አይቀሬ ነው። .
« እናንተም እረሱ እኛም እናርሳለን
መኸር ሰብሳቢውን አብረን እናያለን» ….ወዳጄ ኮሜዲያን አብርሃም አስመላሽ (አፈሩን ገለባ ያድርግለት) ለገዢው ተላላኪዎች በምሬት የተናገረው።

የመኢአድ እና አንድነት ዉህደት ለማጨናገፍ ችኮላው ለምን? (አልዩ ተበጀ)

$
0
0

አልዩ ተበጀ

አብዛኞቻችን የአንድነት እና መኢአድ ዉህደት ተጠናቆ፣ በአዲስ መንፈስ የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄን እንቀጥላለን የሚል ተስፋና ጉጉት ነበረን። የኢትዮጵያዉያንን መተባበር የማይፈልገው ሕወሃት/ኢሕአዴግ፣ በሚቆጣጠረው ምርጫ ቦርድ አማካኝነት፣  ዉህደቱን ለማጉዋተት እንደተለመደው መስራት ጀመረ። «መኢአድ ያላሙዋላቸው ወረቀቶች አሉ» በማለት ዉህድቱን ማድረግ እንደማይችል አሳወቀ። (የተለመደው የማሰናከል እጁት ተግባር) መኢአድ ሕዝብ ያውቀው ዘንድ፣  ያለውን ሁኔታ ለማሳወቅ መግለጫ አወጣ። በጉዳዩ ላይም ከምርጫ ቦርድ ጋር ስብሰባዎች በማድረግ ከመፍታት ጀምሮ ሌሎች አማራጮችን እየፈለገ ዉህደቱን ለማሳካት በስፋት መንቀሳቀስ ጀመረ።

ከመኢአድ ጋር ዉህደት ለማድረግ ከ2 ፣ 3 አመታት በላይ ንግግሮች ሲደረጉ ነበር። አገዛዙ የደነቀረዉን ትንሽ እንቅፋት ለማስወገድ አንድ ወይንም ሁለት ሳምንት መጠበቁ ችግር የሚኖረው አይመስለኝም። ነገር ግን እንደ አንድነት ደጋፊ እጅግ በጣማ ያሳዛነኝ እና ልቤን ያደማው ክስተት ተፈጸመ።

የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው፣ ለብዙ አመት የተደከመበትን፣ የዉህዱ ሰብሳቢ ሊቀመንበር የነበሩት አቶ ሃብታሙ አያሌው የታሰሩበትን ፣ በአገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በጉጉትና በተስፋ የምንጠብቀዉን፣ ምርጫ ቦርድ ካስቀመጣት ትንሽ መሰናክል ዉጭ፣ ሁሉም ነገር ያለቀለትን፣ የመኢአድ እና የአንድነት ዉህደት እንደማይፈልጉ በመገልጽ የዉህደት አመቻች ኮሚቴን እንዳፈረሱ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

በሚኔሶታ  ቤተክርስቲያን ስሄድ ፣ የአንድነት ድጋፍ ድርጅት አስተባባሪ መሆኔን የሚያዉቁ ሲያገኙኝ ፣ አንድነት ከመኢአድ ጋር የሚያደርገውን እንቅስቅሴ እንደተደሰቱ ነበር በስፋት የሚነግሩኝ። ህዝቡ፣ ደጋፊው ስሜቱ በጣም ተጋግሎ ነበር። በአሁኑ ጊዜ የሕዝቡ መከራ በበዛበት፣ አንድነት ፓርቲ ሌሎችን እያሰባሰበ፣ የተጀመረዉን የሚሊዮኖች ንቅናቄ ይቀጥላል ብለን ስንጠብቅ፣ ያለ ምንም በቂ ምክንያት ሕወሃት/ወያኔ ትንሽ መሰናክል ስላስቀመጠ ብቻ ፣ በየክልሉ ያሉ አባላትና ደጋፊዎች እየፈለጉት፣ ዉህደቱ እንዲቆም ማድረግ በጣም፣ እጅግ በጣም ትልቅ በደል ነው።

በአንድነት እና በመኢአድ መካከል፣ ዉህደት እንዲደረግ ቁልፍ ሚና ከተጫወቱት ወገኖች መካከል አንዱ፣ በሕወሃት/ኢሕአዴግእጅ ስር ታስሮ የሚገኘው ሃብታሙ አያሌው ነው። ሃብታሙ አያሌ ከኢንጂነር ግዛቸው ጋር ብዙ ይከራከር የነበረና ኢንጂነሩም ለሚሰራው ስራ መሰናክል ሆነውበትምእንደነበረ ይታወቃል።  ከአምስት አመታት በፊት፣ ኢንጂነር ግዛቸው ከትናትናው “ዝምአንልም” የዛሬው በአብዛኛውየሰማያዊ አመራሮችአባል ከሆኑት ጋር ተመሳሳይ ችግር እንደነበረባቸው የሚታወቅ ነው:: እነዚህን በርካታ ወጣት የቀድሞ የአንድነት አመራሮችን፣   እንዲሁም እንደ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ያሉትን ማባረራቸው ይታወቃል። ያኔ ፓርቲው ተከፋፍሎ በትግሉና በታጋዮች ሞራል ዘንድ ምን ያህል ከፍተኛ አሉታዊ ተጽእኖና ጉዳት እንዳመጣም የሚታወቅ ነው።

ኢንጂነር ግዛቸው የመኢአድ እና የአንድነት ዉህደት እንዲኖር ፍላጎት  ብዙ እንዳልነበራቸው የሚናገሩ አሁንምጥቂቶች አልነበሩም። (ዉህደቱ ከተሳካ ሊቀመንበር የመሆን እድላቸው በጣም የመነመነ በመሆኑ) የምርጫ ቦርድንም ተንኮል ሳያጡትቀርተው አደለም፣  ምርጫ ቦርድ ለአገዛዙ እንደሚሰራ እያወቁ፣ ምርጫ ቦርድ የሚያቀርባቸውን እንቅፋቶች እንደ ሰበበ በመቁጠር የዉህደት አመቻች ኮሚቴዉን ማፍረሳቸው፣  እንደ አንድ የአንድነት ደጋፊ ልረዳው የማልችለው ጉዳይ ነው። በሚሊዮኖች ዘመቻ የተነሳሳዉን፣  በሚሊዮኖች የሚቆጠር ኢትዮጵያዊ ወኔ ለማኮላሸት፣ ከትግሉና ከአገር ጥቅም ይልቅ የራሳቸውን ስልጣን ብቻ በመፈለግ ለሕዝብ ጥያቄ ንቀታቸውን በመግለጽ ትልቅ ጥፋት እያደረጉ ናቸው።

ሕዝቡ አብሮ መስራትን ይፈልጋል። የመኢአድ እና አንድነት ዉህደትን ይፈልጋል። የማይፈልጉት አምባገነኖች ብቻ ናቸው። ኢንጂነር ግዛቸውና ለርሳቸው ድምጽ የሰጡ የአንድነት የምክር ቤት አባላት፣ «ሕወሃት/ሕአዴግን የሚያስደስተዉን ነው ወይስ ህዝቡ የሚያስደስተው ማድረግ የምትፈልጉት ?» ለሚለው ጥያቄ በግልጽ ሊመልሱ ይገባል።

በኢንጂነር ግዛቸው የተወሰደው ሕወሃት/ሕአዴግን ብቻ የሚጠቅም እርምጃ በአስቸኩዋይ ተቀልብሶ ፣ አንድነት ከመኢአድ ጋር የጀመረዉን ዉህደት አጠናቆ፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ አፍሮ፣ ትግሉ ወደፊት መዉሰዱ ብቸኛ አማራጭ ነው።

ኢንጂነር ግዛቸው ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ችግር አላቸው። አሁን ደግሞ ከመኢአድ ጋር ከተጣሉ፣ ታዲያ እመራዋለሁ የሚሉት አንድነት ከማን ጋር ነው አብሮ የሚሰራው ? በዘር ከተደራጁ ድርጅቶች ጋር ? ወይስ ተመልሰው ወደ መድረክ በመግባት የ2002ቱን ሩጫ ሊደግሙልን ነው ?

የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች፣ እኛ በሚሊዮኖች የምንቆጠር ነን። ወሳኝ ጊዜ ላይ ነው ያለነው። ጥቂቶች ንቅናቄያችንን ወደሁዋላ ሊጎትቱ አይገባም።በመሆኑም ከመቼዉም ጊዜ በላይ ድምጻችንን ማሰማት አለብን። የአንድነት ፓርቲ የኢንጂነር ግዛቸው ብቻ ሳይሆን የሚሊዮኖች ነው። በደሴ፣ በጎንደር፣ በአርባ ምንጭ፣ በናዝሬት፣ በባህር ዳር፣ በአዳማ ..የምንኖሩ የአንድነት አባላትን የክልል አስተባባሪዎች፣ በዉጭ አገር ያለን  ድምጻችንን እናሰማ። በየአካባቢያችን ከመኢአዶች ጋር አብረን በስራ ተዋህደን እየሰራን ነው። አብረን እየታሰርን፣ አብረን እየተደበደብን  ነው። አገዛዙ ከሚያደርገው በማይተናነስ ሁኔታ ኢንጂነር ግዛቸውና ከርሳቸው ጋር የቦደኑ ጥቂቶች እንዲከፋፍሉን መፍቀድ የለብንም። አንድነታችንን ለማሳየት የምርጫ ቦርድ ወረቀት አያስፈልገንም። ትግሉን ተያይዘን መቀጠል አለብን። ትግሉ የሚሊዮኖች ንቅናቄ ነው። ትግሉ ወደፊት እንጂ ወደ ሁዋላ አይሄድም ።

 

udJ&AEUP

አቶ በረከት ከአንድ ወር በኋላ ለምርመራ ወደ ሳዑዲ አረቢያ እንደሚመለሱ ተገለጸ፤ ግማሽ ሚሊዮን ብር ለህክምናቸው ወጪ ሆኗል

$
0
0

bereket simon
ከኢትዮጵያ ሃገሬ ጅዳ በዋዲ

የልብ ህክምናቸውን ጨርሰው ሰሞኑን ወደ ኢትዮጵያ ያቀኑት አቶ በረከት ስሞዖን የጤንነታቸው ሁኔታ ከበፊቱ በተሻለ ሁኔታ ላይ መሆኑን የሚያመለክቱት በሳውዲ አረቢያ «የቡግሻን» ሆስፒታል ምንጮች ባለስልጣኑ በአፋጣኝ ህክምና ተደርጎላቸው ባይሆን ኖሮ በሽታው ሙሉ ለሙሉ ሽባ « ፓራላይዘድ » ሊያደርጋቸው ይችል እንደ ነበር ይገልጻሉ።

ሳውዲ አረቢያ ጅዳ ከተማ የሚገኝ በተለምዶ «ቡግሻን ተብሎ የሚጠራ ሪፈራል hospital » ውስጥ የኚህን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን የልብ ችግር ለመፍታት ከ 6 ሰዓታት በላይ ህክምና መውሰዱን የሚናገሩ የሆስፒታሉ ምንጮች የልብ ቦንቦውን የምሳፋት ስራ የተሳካ እና ጥንቃቄ የተሞላበት ቢሆንም አቶ በረከት የጤንነት ሁኔታቸው በማህበራዊ ገጾች መነጋገሪያ መሆኑ ተከትሎ በውስጣቸው የፈጠረው ጭንቀት ከህክምናው በኃላ የልብ ምታቸው ለውጥ ባለማሳየቱ በህክምና ባለሙያዎቹ ላይ ከፍተኛ ድንጋጤን ፈጥሮ እንደነበር አክለው ገልጸዋል ። በልብ ዙሪያ የሚከሰቱ ችግሮች ዋስትና እንደሌላቸው የሚናገሩ አንዳንድ የሙያው ጠበብቶች የልብ ቦንቦ ቸገር አብዛኛውን ግዜ የሚከስተው ከውፍረት እና ከደም መርጋታ ጋር ተያይዞ መሆኑን በመጥቀስ በሽታው « በግራ በኩል የሚገኘውን የሰውነት ክፍል ባልታሰበ ግዜ ሙሉ ለሙሉ ሽባ « ፓራላይዝድ በማድረግ እስከሞት ሊያደርስ የሚቸል አደገኛ በሽታ መሆኑን በመጥቀስ።

በተመሳሳይ መልኩ የኚህን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን የጤንነት ሁኔታ በቀጣይነት ለማረጋገጥ፡በየወሩ ምርመራ ማድረግ እንደሚገባቸው ይናገራሉ ። ሰሞኑንን ባህርዳር የብሄር አማራ ዴሞክራሲ ንቅናቄ « ብ.አ.ዴ.ን » ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ሊትዮጵያ ህዝብ በመንግስት መገኛኛ ብዙሃን የታዩት አቶ በረከት የፊታቸው ገጽታ መልካም ጤንነት ላይ መሆኑን ቢገልጽም በአጋጣሚ ህይወታቸውን ሊያሳጣቸው ከሚችለው የልብ በሽታ እራሳቸውን ለመታደግ የጤና ምርመራ «ቼክ አፕ» ለማድረግ ከወር በሃላ ወደ ሳውዲ አረቢያ እንደሚመለሱ ለማወቅ ተችሎል።

የአቶ በርከት ስሞዖን ቀጣዩ የሳውዲ አረቢያ የጤና ምርመራ ጉዛ ጅዳን አልፎ ሪያድ ሊዘልቅ እንደሚቸል የሚገልጹ ውስጥ አውቂ ምንጮች እኚህን የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣን ሼክ አላሙዲን በሳውዲ መንግስት በኩል በፕሮትኮል ለማስገባት እቅድ እንዳላቸው አክለው ተናግረዋል። በሼኽ አላሙዲን የግል አይሮፕላን በድብቅ ሳውዲ አረቢያ ገብተው ህክምናቸውን ሲከታተሉ ለቆዩት አቶ በረከት ስሞዖን እስካሁን 60 ሺሕ የሳውዲ ሪያል (60 ሺህ ሪያል በአሁኑ የኢትዮጵያ ምንዛሪ « ግማሽ ሚልዮን ብር » ነው) መውጣቱን እና ጠቅላላ የህክምን ወጪውም በሼኩ ሙሉ ለሙሉ መሸፈኑን ለማረጋገጥ ተችሏል።

ፕሬስ የሌለው መንግስት ከሚኖረን መንግስት የሌለው ፕሬስ ቢኖረን እንመርጣለን

$
0
0

ዳዊት ሰሎሞን

10570542_10204024912521089_4618968976545930065_nእርግጥ ነው የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጆች ለስደት ሲዳረጉ ‹‹አዲስ ዘመንንም አዲስ ነገርንም አላነብም››በማለት ነግረውን ነበር፡፡ሌጋሲያቸውን ለማስቀጠል ቤተ መንስግስት የገቡት ሃይለማርያም በበኩላቸው በአንድ ጋዜጣዊ መግለጫ የፎርቹንን ኮሪደር እንደሚያነቡ ሲናገሩ አድምጫለሁ፡፡

የቅንጅት አመራሮች በድርድሩ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ እንደገቡ ብዛት ያለው የኢትዮ ቻናል ጋዜጣ ተጠርዞ መመልከታቸውን መናገራቸውም አይዘነጋም፡፡ገዢዎቻችን ከቀድሞዎቹ ነገስታት ባነሰ መልኩ ‹‹አዝማሪ ምን አለ?››በማለት ለመጠየቅ አለመፍቀዳቸው ትርጉሙ ንቀት ብቻ ነው፡፡ህዝቡን የሚፈልጉት እነርሱ

ሲናገሩ እንዲያደምጥ ብቻ እንጂ ሲናገር ሊሰሙት አይደለም፡፡ስለዚህ ጋዜጦችን አያነቡም፡፡የማያነቧቸውን ጋዜጦች አዘጋጆች ለስደት ሲዳረጉ ደግሞ ቅንጣት ታህል አትሰማቸውም፡፡
በጥቂት ወራት ውስጥ የተደረጉ ፕሬስን ከአገሪቱ ገጽ ለማጥፋት የተወሰዱና እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን ተመልከቱ፡፡ጋዜጠኞች ተሰባስበው ለመመስረት ቀና ደፋ ያሉለት አዲስ ማህበር እውቅና ተነፈገው፣የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና ሶስት ጋዜጠኞች ለእስር ተዳረጉ፣ትግራይን ህዝብ ፍዳ በሶሻል ሚዲያ ሲያጋልጥ የቆየው አብርሃ ደስታ ጨለማ ቤት ተወረወረ፣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አስጠናሁ ያለውን ወረቀት አቅርቦ ጋዜጦችን በኒዮ ሊበራሊስትነት ከሰሰ፣ከጫካ ጀምራ የህወሃት አፍ የነበረችው ፋና የጋዜጣ አከፋፋዮች ላይ ዘመቻ ከፈተች፣ዘመቻውን ተከትሎ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ አከፋፋዮችና ጋዜጣ አዟሪዎች ስቅይት ደረሰባቸው፣ፍትህ ሚኒስትር የህትመት ውጤቶች አሳታሚዎች ላይ ከፍተኛ የወንጀል ክስ መመስረቱን ነገረን፣ክሱ መነገሩን ተከትሎ ማተሚያ ቤቶች ጋዜጦችን የማስተናገድ ፍርሃት ወረራቸው አንዳንዶቹም በግልጽ ይህን ጋዜጣ እንዳናትም ቀጭን ትዕዛዝ ደርሶናል አሉ፣ካፌዎች በግድግዳቸው ላይ ‹‹ጋዜጣ ባለማንበብዎ እናመስግናለን እና ጋዜጣ ማንበብ አይቻልም››የሚሉ ማስታወቂያዎችን መለጠፍን ስራቸው አደረጉት ፡፡

ስደት ብርቃችን አይደለምና ይህው የተወዳጇን አዲስ ጉዳይ መጽሔት ባለቤትና አዘጋጆች ስደት ሰማን ፡፡ይህ ለኢህአዴግ ምኑ ነው?ፕሬስ የሌለው መንግስት እንዲኖረን የሚፈልግ በመሆኑ ደስታውን የሚችለውም አይመስለኝም፡፡ኮካዎች ምን ትላላችሁ?

አዲስ ጉዳይ ተሰደደች ”ምርጫ መጣ ፕሬስ ውጣ”

$
0
0

10570542_10204024912521089_4618968976545930065_nበአዲሳባ እና በመላው ሀገሪቱ ከፍተኛ ተነባቢነት ካላቸው መጽሄቶች ተርታ የምትመደበው አዲስ ጉዳይ አዘጋጆች መሰደዳቸው ተሰማ። መንግስት አዲስ ጉዳይን ጨምሮ በበርካታ ጋዜጦች እና መጽሄቶች ላይ ክስ ሊመሰርት መሆኑ በተሰማ ማግስት ”ምርጫ መጣ ፕሬስ ውጣ” የሚል ጽሁፍ ያስነበበችን አዲስ ነገር ከመታሰር አለመታስር ይሻላል ብላ መሰደድን መርጣለች።

ደረጄ ሀብተወልድ እንደነገረን የመጽሔቱዋን ባለቤት እንዳልካቸው ተስፋዬን ጨምሮ የመጽሔቱዋ ምክትል ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ኢብራሂም ሻፊ፣ ከፍተኛ አጋዘጅ ጋዜጠኛ እንዳለ ተሽ እና አዘጋጅና አምደኛ ሀብታሙ ስዩም በፕሬሶች ላይ እየተንደረደረ በመምጣት ላይ የሚገኘውን የክስ ናዳ ”ሽል” ብለው አምልጠውታል።

10155812_762741180411560_2062798175_n-150x150በቅርቡም የሰንደቅ ጋዜጣ ከፍተኛ አዘጋጅ የነበረው ዘሪሁን ሙሉጌታ እየደረሰብት ያለውን የደህነነቶች ጭቅጭቅ እና ንትርክ እንዲሁም የእስር እና እንግልት ስጋት ሽሽት ሀገሩን ለአስር አለቆች ትቶ መውጣቱን አለመዘገባችን ይታወቃል። (በቀንፍም እንዲህ እያደራጁ መዘገብ ሳይሻል አይቀርም ብለን በማይቀለደው እንቀልዳለን)

ሰዎቹ ሁሉን አባረው ሲያበቁ የእስር ሱሳቸውን ርስ በርስ በመተሳሰር ይወጡት እንደሁ እናያለን እንግዲህ!

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ብሔራዊ ምክር ቤት ሁለት ውሳኔዎችን አስተላለፈ

$
0
0

10606470_681304371954500_7184262179990938183_nየአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ብ/ም/ቤት ነሐሴ 04 ቀን 2006 ዓ.ም የጠራው አስቸኳይ ስብሰባ ሁለት ውሳኔዎችን በማስተላለፍ ስብሰባውን በተሳካ ሁኔታ አካሂዷል፡፡
በዚህም መሰረት ጠዋት የተደረገውን ስብሰባ የመሩት አቶ አበበ አካሉ የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ ሲሆኑ፣ ምክር ቤቱ የተወያየበት አጀንዳ የመኢአድና የአንድነት የውህደት ሂደትና የተደረሰበትን ውጤት መርምሮ አቅጣጫ ማስያዝ ሲሆን በተደረገውም ሰፊና ጥልቅ ውይይት
- የምርጫ ቦርድ ለመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በደንቡና በአዋጁ መሰረት እንዲያሟላቸው የጠየቃቸውን ጉዳዮች እስኪያሟላ ድረስ በአንድነት ፓርቲ ደንብና መመሪያ መሰረት ውህደትን በሚመለከትና አዘጋጅ ኮሚቴ መወከል የብሔራዊ ም/ቤት ሥልጣን በመሆኑ ም/ቤቱ የወከለው የጠቅላላ ጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ለጊዜው ስራውን እንዲያቆም ውሳኔ በማስተላለፍ ከመኢአድ ጋር የሚደረገው ውህደት በማንኛውም ጊዜ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል፡፡
- በመቀጠልም የአንድነት ፓርቲ መዋቅራዊ አካላት የሥራ እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት እንዲመለስና ከብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ጀምሮ እስከ ዝቅተኛው መዋቅር ድረስ የወጡትን የሥራ ዕቅዶች እንዲያከናውኑ ም/ቤቱ መመሪያ ሰጥቷል፡፡
የከሰዓት በኋላ የም/ቤቱን ውሎ የመሩት የም/ቤቱ ም/አፈ ጉባኤ አቶ ደምሴ መንግሥቱ ሲሆኑ የውይይቱ አጀንዳም የፓርቲው የመገናኛ ብዙኃን እንዲመራ ኃላፊነት የተጣለበት ኤዲቶሪያል ቦርድን በተመለከተ ነበር፡፡
- ም/ቤቱ በተደረገው ውይይት ቀደም ሲል የተቋቋመው ቦርድ በአጠቃላይ የፈጸማቸውን የሥራ ክንውን፣ ጠንካራና ደካማ ጎኖች በተመለከተ ሪፖርት እንዲያዘጋጅና በሚቀርበው ሪፖርት መሰረት ተወያይቶ በአዲስ መልክ የኤዲቶሪያል ቦርድ አባላትን ለማቋቋም ለነሐሴ 18 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጠሮ በመያዝ ስብሰባው ተጠናቋል ሲሉ አቶ ደምሴ መንግስቱ የብ/ም/ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡

Millions of voices for freedom – UDJ

ኢንጂነር ግዛቸው የመኢአድ/አንድነት ዉህደት አመቻች ኮሚቴን አፈረሱ

$
0
0

10590397_1465508690367579_46579675110189955_n

ኢንጂነግር ግዛቸው በሕዝብ ዘንድ በጉጉት የሚጠበቀዉን፣ ለአገዛዙ ራስ ምታት የሆነው፣ የመኢአድ እና አንድነት ዉህደት አመቻች ኮሚቴን አፈረሱ። በአባላትና ደጋፊዎች ዘንድም ትልቅ ድንጋጤ ተፈጥሩዋል። በአገዛዙም ዘንድ ደስታው ጨምሩዋል።

– በዉጭ አገር ያሉ የአንድነት ደጋፊዎች በኢንጂነር ገዛቸው ላይ ከፍተኛ ተቃዉሞ እያሰሙ ናቸው።

የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ፣ አቶ ተስፋሁን አለምነህ፣ ለሕብር ራዲዮ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ የአንድነት እና መኢአድ ዉህደት የሕዝብ ጥያቄ እንደሆነ ገልጾ፣ ገዢው ፓርቲ ምርጫ ቦርድን ተጠቅሞ የሚያስቀምጣቸው መሰናክሎችን አጥብቀው እንደሚያወግዙ ገልጸዋል። ድርጅታቸው አቶ አበባው መሐሪን ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ ሲመርጥ፣ የምርጫ ቢርድ ሃላፊዎች በተገኙበት የተደረገ እንደሆነ የገለጹት አቶ ተስፋሁን፣ አገዛዙ ዉህድቱ እንዳይሳካና ተቃዋሚዎች ተከፋፍለው እንደለመደው የ2007 ምርጫን አጭበርብሮ ለማሸነፍ ሲል፣ ሆን ብሎ እያደርገ ነው ሲሉም ከሰዋል።


መኢአድ ሰላማዊ ሰልፎችን፣ የሥራና የትምህርት ማቆም አድማዎችን እንደሚጠራ የገለጹት ቶ ተስፋሁን፣ ትግሉ የሚጠይቀው ማናቸዉን መስወአትነት ለመክፈል አመራሩ እንደተዘጋጀም አስረድተዋል።
የመኢአድ እና የምርጫ ቦርድ ፍጥጫ በዚህ ሁኔታ እንዳለ ፣ ከመኢአድ ጎን በመቆም አጋርነት ይገልጻሉ፣ ምርጫ ቦርድ ላይ በጋራ ጫና ለማድረግ ድርጅታቸው ያሰልፋሉ ተብለው የሚጠበቁት፣ ኢንጂነር ግዛቸው፣ ከአንድ ሳምንት በፊት አገር ዉስጥ ላሉ ጋዜጦች የሰጡትን አስተያየት በመቀልበስ፣ የዉህደት አመቻች ኮሚቴዉን ያፈረሱ ሲሆን፣ ለውህደት በሚደረገዉ ከፍተኛ ትንቅን ላይ ቀዝቃዛ ዉሃ ከልብሰዉበታል።


«ኢንጂነር ግዛቸው በአሁኑ ወቅት ከመኢአድ ጋር በመሆን፣ በጋር የሚሊዮኖች ንቅናቄን በማጡዋጣፍ ፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ፣ በምርጫ ቦርድና አገዛዙ ላይ ጫና ማሳደር ሲገባቸው፣ የዉህደት አመቻች ኮሚቴውን ማፍረሳቸው ሰላማዊ ታጋዮች አንገት የሚያስደፋ ነው» ያሉት በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የፖለቲካ ተንታኝ የኢንጂነሩን ዉሳኔ የሚረዳዉና የሚጠቅመው አገዛዙን ብቻ እንደሆነም ይናገራሉ።
ከኢንጂነር ገዛቸው አመራር ጋር በተገናኝም በዉጭ አገር የሚኖሩ የአንድነት ደጋፊዎች በኢንጂነር ግዛቸው አመራር ላይ ያላቸውም ከፍተኛ ተቃዉሞ እየገለጹ መሆናቸውን ለመረዳት ችለናል።

Source abugidainfo.com


6 የአንድነት ከፍተኛ አመራሮች ከኢንጂነር ግዛቸው ካቤኔ ራሳቸውን አገለሉ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ኢንጂነር ግዛቸው በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተስፋ የተጣለበትን የአንድነት እና የመኢአድን ፓርቲዎች ውህደት አመቻች ኮሚቴ ካፈረሱና በርካታ ሕዝብን አሳዝነዋል ከተባለ ወዲህ የርሳቸው ካቢኔ ሆነው በአንድነት ውስጥ እያገለገሉ ከሚገኙት ውስጥ 5ቱ ራሳቸውን ማግለላቸውን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው ዜና አመለከተ።
GizachewShiferaw
ራሳቸውን ከኢንጂነር ግዛቸው ካቤኔ ያገለሉትና ለኢንጂነሩም ደብዳቤ ያስገቡት የአንድነት ከፍተኛ አመራር አባላት

  1. ተክሌ በቀለ –ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት
  2. በላይ ፈቃዱ —ምክትል ፕሬዘዳንት
  3. ሰለሞን ስዮም —የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ
  4. ዳንኤል ተፈራ — የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ
  5. ዳዊት አስራደ —የኢኮኖሚ ጉዳዮች ሀላፊ
  6. ፀጋየ አላምረው –የገንዘብ ክፍል ሃላፊ              መሆናቸው ታውቋል።

ከመኢአድ ጋር የሚደረገውን ውህደት እንዲኮላሽ አድርገዋል እየተባሉ የሚተቹት ኢንጂነር ግዛቸው በአስቸኳይ ስልጣናቸውን እንዲለቁ ግፊቱ የጨመረ መሆኑን ያስታወቁት የመረጃ ምንጮቻችን፤ አስተያየት ሰጪዎች በተለይ በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ጃንዋሪ 12 ቀን 2014 የሰጡት ቃለምልልስ ላይ ያሉትን በመጥቀስ “ይህን ካደረግኩ በኋላ ከኢሕአዴግ ጋር ገንቢ ግንኙነት (Constructive Engagement) እንዲኖረን እፈልጋለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የጥላቻ ፖለቲካ ማብቃት አለበት፡፡ ኢሕአዴግ ተቃዋሚዎችን የሚያያቸው እንደ ጠላት ከዚያም አልፎ እንደ ሽብርተኛ ነው፡፡ ይኼንን ነገር ለሚያስብ ሰው እኮ በጣም ነው የሚያስደነግጠው፡፡ በእኛም በኩል ኢሕአዴግን የምናየው እንደ አውሬ ነው፡፡ ምናልባት የሠራውን ሥራ ሁሉ ዋጋ (Credit) ያለመስጠት አለ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፖለቲካችን ኢሕአዴግን መቃወም ብቻ ሆኖአል፡፡ ያ መቆም አለበት፡፡ ትልቁ ኳስ ያለው ኢሕአዴግ ዘንድ ነው፡፡ እኔ በበኩሌ ወደፊት በማደርገው እንቅስቃሴ ገንቢ ግንኙነት አድርገን ያለውን የፖለቲካ ምኅዳር ለሁላችንም እኩል ማድረግ አለበት፡፡” የሰውዬው አካሄድ ወዴት ነው እያሉ እንደሚነጋገሩበት አስታውቀዋል።

በትግራይ ክልል አራት መቶ ሺ ህዝብና በሚሊየን የሚቆጠሩ የቤት እንስሳትን የሚቀልብ በለስ ወደመ

$
0
0

ዜና ትንታኔ በአስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል

ከመቐለ

አቶ አስገደ ገ/ስላሴ

አቶ አስገደ ገ/ስላሴ

በትግራይ ክልል በምስራቃዊ ሰሜን፣በደቡባዊ ምስራቅ በደቡብ ዞኖች የሚኖሩ ከ 1.5 ሚሊየን የሚቀጠሩ እንስሳ ዘቤት የሚቀልብ በለስ የሚባል እፅዋት የህዋሃት መሪዎችና እነሱ የሰርዋቸዉ ደንቆሮ የሳይንስ ተመራማሪ ተብዬዎቹ ሃርና ቀለም ከበለስ አፍርተን ትግራይን ሃብታም እናደርጋታለን በሚል ጥናት የጎደለዉ አውዳሚ ባክቴርያ (ቫይረስ) ሊሆን ይችላል አስገብተዉ በበለስ እፅዋት በማራባታቸዉ ያ የተራባዉ ባክቴርያ ሃር ሳይሆን አመረተዉ ለዚሁ ለተጠቀሰዉ ህዝብ ከ 6ት ወር በላይ 95% የምግብ ፍጆታዉን ይሸፍናል። ሁሉም እንስሳ ዘቤትም አመት ሙሉ ከመመገባቸዉ ህዝሠቡ ለራሱ ለምግብነት ከመጠቀሙ አልፎ ለገበያ እየወረደ በመላዉ የኢትዮጵያ ክልሎች በማሰራጨትበመሸጥ ብዙ ብር ያፍስ ነበር። የነዚህ አካባቢ ህዝብ ከሚያዚያ ወር ግማሽ እስከ ጥቅምት ወር ከላይ እንደጠቀስኩት በሚመገቡት በለስ ነበር።

ስለ በለስ ጥቅም የትግራይ ክልል መሪዎች የነሱ ስሪት ምሁሮች የነሱ ተላላኪዎች የመቐለ ዩኒቨርሲቲ በለስ ተመራማሪዎች ምንም መነሻ የሚሆን የሳይንስ ግኝት በተጨባጭነት የሌላቸዉ ከበለስ ይህን የሚያክል ቶንክ ሃር ቀለም ማርማላት በማምረት በመቶ ሽዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች ስራ እንፈጥራለን እያሉከ 13 አመት በላይ በነዛ የፈለጉት ውሸትና ማደናገሪያ ዲስኩራቸዉን የሚያሰራጩባቸዉ ሚድያዎች አድርገዉ ለትግራይ ህዝብ የህልም እንጀራ ያበሉት ነበር።ሌላ ቀርቶ የበለስ ግንድ በመቁረጥ ለምግብነት ለመጠጥ ፣ ለማርማላት ይጠቅማል ተብሎ ለሁሉም ፕሮጀክቶች የሚያስተባብሩ ቢሮ ተመስርቶ ከእርዳታ ሰጪ አገሮች ብዙ ውሸት የውሸት ፕሮጀክቶች እያዘጋጁ እርዳታም ያገኙ ነበር። ውጭ አገር እየሄዱም ስለ በለስ ምርምር ለልመና እንዲመቻቸዉ ብዙ የሃገራችን የውጭ ምንዛሪ በልተውታል ሰብስበውታል የየግላቸዉ ህንፃ ሰርተዋል።

ይህ ሁሉ የደንቆሮ ምርምር አሁን ተጋለጠ

የህወሃት ግብታዊ የሆነ የሳይንስ ግኝት ያሃርና ቀለም ያመርታል ብለዉ ያመጡት ክንችያ የተባለዉ ባክቴርያ በመቶ ሺ አመት የሚቆጠር ህዝቦች ከአመት የምግብ ፍጆታ ከ 60% የሚጠቀሙበት በባክቴርያ ወድሟል እየወደመም ይገኛል። ለዚሁ ለማስረጃነት በትግራይ ክልል ደቡባዊ ምስራቅ በደቡብ በተለይ በራያ መኾኒ ወረዳ በሕንጣሎ በአላጀ እንዲሁም በከፊል እንደርታ ወረዳ አፅቢ ወንበርታ ወረዳዎች ስፋቱ 300 ኪሎ ሜትር ቁመቱ 300 ኪሎ ሜትር ስፋት ( 36000 ስኴር ኪሎ ሜትር መሬት የበቀለ በለስ ሙሉ በሙሉ ወድሟል። ይህ እፅዋት ሞቶ እንደተጣለ እንስሳ በለስም ወደመ።በነዚህ አካባቢ የሚኖሩ ዜጎች ተርበዋል እንስሶችም የሚበሉት አጥተዉ እየሞቱ ይገኛሉ።ለህዝብ የሚበላ ለእንስሳ መኖ የሚሰጥ ወገን የሚሰማቸዉ መሪዎች የሉም። በተለይ ደግሞ ትልቅ አደጋ ደርሶባቸዉ በሞዴልነት ለመጥቀስ በድሮ የዋጅራት ወረዳ ደቡብ 76000 ዜጎች ለመጥቀስ በራያም እንደዚሁ መኾኒ ወረዳና አካባቢዋ ከ 80000 ህዝብ በላይ ረሃብ ላይ ወድቀዋል እንስሳት እየሞቱ ናቸዉ።

የትግራይ ክልል ባለስልጣናት ተመራማሪ ሳይንቲስቶች በህዝባችንና በንብረቱደርሶ ላለዉ የምርምራቸዉ ውድቀት አሳፍሯቸዉ ለሁኔታዉ ተቆርቋሪ ሆነዉ ከመቅረብ ዝምታን መርጠዉ ድምፃቸውን ደብቀዉ ይገኛሉ ።ህዝቡ ግን በተለይ የሕንጣሎ ዋጅራት የመኾኒ ወገኖች እስከ የክልሉ ፕሬዚደንት ኣባይ ወልዱና ኪሮስ ቢተዉ ኣቤት ቢሉም ሰሚ ጆሮ አላገኙም።

የዋጅራት ህዝብ በበለስ መውደም ብቻ አይደለም የከሰረዉ ሰፊ የእርሻዉ ማሳዉ መቐለ ለሚገኘዉ ስሚንቶ ፋብሪካ የሚጠቅም አፈር ስላለዉ ኢፈርት ምንም ግምት ሳይሰጥ መሬቱን ቀምቶት ይግኛል። ከዚህ አፈር የተወሰነ ኮሚሽን እንኳ ቢከፈለዉ ለ 76000 የዋጅራት ህዝብ ይቀበለዉ ነበር ኢፈርት ግን አንድ 2ጃ ደረጃ ት/ቤት ሰርተንላችሁ በማለት እያተላሉዋቸዉ ይገኛሉ። እነዚህ ዜጎች የይገባኛል ጥያቄ ሲያነሱም ብዙ ሰዎች በማሰር ሽብር ፈጥራቹሃል ተብለዉ በእስር ተሰቃይተዋል ለአፍ ጉርስ በማጣ ታቸዉ አዛውንት ሴቶች ህፃናት ለስደት ሲፈልሱ ወጣቶች ወ ደ አረብ አገር ተሰደዉ ሲሰቃዩ ለነዚህ ወገኖች እንደ ማዘን ፈንታ በነዛ እኛ ባልናቸሁ ተንፍሱ ተብለዉ የሚታዘዙ የመንግስትና የፓርቲ ሬድዮ ጣቢያዎች ከኤፍኤም ቴሌቪዢን አድርገዉ እነዚህ ለልመና ለስደት የሚፈልሱ ሰዎች ባቋራጭ ለማደግ የሚፈልጉ ተብለዉ ሰብኣዊ መብታቸዉ ተነክተዋል። በተለይ ደግሞ ሰሓረቲ ሳምረ ወረዳ ነዋሪ የሆኑ ወገኖች እጅጉን ሃብታሞች ነበሩይሁን እንጂ በ 17 አመቱ የትጥቅ ትግል ጊዜ ልጆቻቸዉ ወደ ትግል አክትተዉ የተሰዉባቸዉ ቤታቸዉ ተቃጥሎባቸዉ ሃብታቸዉ በደርግ ተወርሶ የቀረረዉ ሃብታቸዉ ለህዋሃት አስረክበዋል። ብዛት ያላቸዉ ወገኖችም ለህወሃት አመራርና ካድሬዎች ጥያቄ አንስተዉ በመቃወማቸዉ ብዙ ታስረዋል ከባድ ቅጣት ተቀጥተዋል ተሰቃይተዋል ባሁኑ ጊዜ ….. እነዚህ ከጥንት ጀምረዉ እምቢ ለጭቆና አንገዛምብለዉ ያምፁ የነበሩ በመሆናቸዉ ይህ መንግስት የነዚህ ወገኖች ጥንካሬ አይፈልግም ያሰጉታና።
mekelle university
አሁን እነዚህ የበለስ አብቃዮችና ተጠቃሚ ወገኖች የነዛ በለሳቸዉ የወደመባቸዉ ዜጎች በመመልከታቸዉ እያነሱት ያለዉ ጥያቄ የህወሃት ስሪት የዩኒቨርሲቲ ምሁራን እርሻና የተፈጥሮ ሃብት ባለሞያዎች ያላነነሱት ጥያቄ ከቺንያ የሚባል ባክቴርያ ወይም (ቫይረስ) 1ኛ ወደ ሁሉ የበለስ አብቃይ ከባቢዎችከተዘመተ የወደፊት እጣ ፈንታችን ምን ይሆን? 2ኛ ወደ ሌላ እፅዋትና የእርሻ ሰብል ክዘመተ እቺ ኣገር ምድረ በዳ ትሆናለች 3 ይህ በሽታ ሂወት ያለዉ እፅዋት አውዳሚ ከሆነ ከሆነ ሰውና እንስሳም ሂወት ያላቸዉ በመሆናቸዉ ለዜጎች ያለዉ ጠንቅነት ምን ሊሆን ይችላል ። ምክንያቱም ባክቴርያዉ በንፋስ ሃይል እየተዘመተ ስላለ አንድ እርምጃ መውሰድ አለበት ይላሉ። የትግራይ የበለስ ተጠቃሚ ወገኖች 4 ይህ እፅዋት አውዳሚ ኤድስ ወደ አገራችን ያስገቡ የህወሃት ባለስልጣናትና ምሁራን ወደ ፍርድ ይቅረቡልን እያሉም ይገኛሉ 5 የዋጀራት ብቻ የወደመው በለስ በመንግስት ትግራይ የተጠናው በኣንድ አመት 750 ሚሊየን ብር የሚገመት ኪሳራ አጋጥሟል የአላጀ፣ የእንደርታ ራያ ዓዲቐይሕ መኾኒ ቤት ማራ የወደመዉ በለስ ሲገመት በቢሊየን የሚቆጠር ብር ነዉ ይህ የእንስሳትና የሰዉ ሞት ሳይጨምር ነዉ።

6 ይህ በሽታ መንግስት ክልል ትግራይ ስላመጣዉ እሱ ወደ ፍርድ ቤት ቀርቦ የፌደራል መንግስት ይድረስልን እያለ ነዉግን ማን ሰማውና?

7 የሃገራችን ህዝቦች ለምን ችግራችንተረድቶ ችግራችን እንዲፈታለን ለመንግስት ተፅኖ አያሳድርም ?አሁንም ይድረስልን እያለ ነዉ

8 የሃገራችን ብቁ ምሁሮች ተመራማሪዎች በነዚህ የህወሃት ስሪት የልማት ሰራዊት ተብዬዎች የደረሰብን ኣደጋ ተረድታችሁ ዝምታን መምረጣችሁ ስህተት ነዉ ይላል የዋጅራት ህዝብ

9 የሃገራችን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለዜጎችህ ፍትህ ነፃነት የመኖር ፣ የመስራት መበት ለማረጋገጥ እንታገላለን እያላችሁ ከ 400ሺ ህዝብ በላይ በከችንያ ኤድስ ህዝብ ቀለብ ሲወድም ዝምታ መምረጣችሁታዲያ ለማን ነዉ የምትታገሉት ብሎ ይወቅሳል

ከላይ የተዘረዘሩት የህዝብ ጥያቄዎች በኔ እምነት ትክክል ናቸዉ እላለሁ። እኔም ባክቴርያዉ ያለ ጥናት ያስገቡ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ተመራማሪዎች የትግራይ ክልል ባለስልጣናት በሙሉ የኪቺኒያ ቫይረስ ሲገባ ትግራይ የሃር ክምር በማምረት በቢሊየን የሚቆጠር ዶላር ገቢ ያገኛል ብለዉ የዋሹ የመንግስትና የፓርቲ ሚዲያዎች ወደ ፍርድ ቤትይቅረቡ የወደመዉ በለስ ካሳ ለህዝቡ ይሰጥ ለዘላቂ ጊዜም መቋቋሚያ ይሰጣቸዉ። የቀረዉ በለስ እንዳይወድም በምን እንከላከለዉ ምን እርምጃ ይወሰድ መልስ ማግኘት አለበት።ለወደመውስ እንዴት ወደ ነበረበት ይመለስ የሚል መልስ ማግኘት አለበት። ሃይለማርያም ደሳለኝም ከአንድ ሚሊየን ህዝብ በላይ አሸብሮ ላለዉ የኪንችያ ቫይረስ እንደ ማሸበር ለሰላም ለሚታገሉ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባላት እያሸበሩና እያሰሩ ይግኛሉ። በመሆኑ ለኪንቺያ ባክቴርያ አለመጋለጣቸዉ ሃይለማርያም ደሳለኝና አለቆቻቸዉም በደረጃቸዉ መፈረድ አለባቸዉ የህግ የበላይነት አለ ከተባለ የሃገራችን የህዝብ ተወካዮች ፓርላማም ይህ አደጋ እያወቀ ዝምታ መምረጡ እጅጉን ሃላፊነት የጎደለዉ ከመሆኑም በተለይ ከሕንጣሎ ዋጅራት ከአላጀ ከመኾኒ ከእንደርታ ከአፅቢ ወንበርታ ወረዳዎች የተወከሉ የፓርላማ አባላት በወከላቸዉ ህዝብ ደርሶ ያለዉ አደጋ አለማጋለጣቸዉና መፍትሄ ለማግኘት አለመጣራቸዉ ለህዝብ ሳይሆን ውክልናቸዉ ለሆዳቸዉ መሆኑ ውክልናቸዉ ያሳያል። በነገብሩ በቀድሞ የትግራይ ክልል መሪዎች ጊዜ የበለስ አትክልት እንደ የድህነት ማጥፊያ ተቆጥሮ በትግራይ ክልል እንዲስፋፋ ይተከል የነበረዉ ከትግራይ አልፈሎ ወደ መላዉ የሃገራችን ክልሎችም እየተቆረጠ ይሄድ የነበረዉ አሁን እንደዚህ ሆኖ የወደመ ዝም ብለዉ ለሚመለከቱ ባለስልጣናት ሃይለማርያም ደሳለኝ እርምጃ እንዲወስድ ካላደረጉ ራሳቸውም ተባባሪ የበለስ አሸባሪ ሆነዋልማለት ነዉ።

የድረሱልኝ ጥሪ

በሃገራችን የሳይንስ ተመራማሪዎች ይህ የበለስ ቫይረስ በበለስ ላይ እያደረሰ ያለዉ ውድመት በሌሎች እፅዋት እንስሳ ሰዉ አደጋ እንዳይደርስ ከአለም አቀፍ የሳይንስ ምርምር በመተግበር ድርሻችሁንብትወጡ ጥርዬን አቀርባለሁ ይህ በሽታ ነገ ሃገራዊ ሊሆን ይችላል።

በትግራይ ክልል በሰሜን ምእራብ ዞን በታሕታይ ቀራሮ በፃዕዳ የእምባ ቀበሌ ( በቖላቑል) የጀመረዉ መድሃኒት ያልተገኘለት ሰዉ ጨራሽ በሽታ አሁን በወልቃይት በፀለምቲ ባድመ አድያቦ አድዋ ተምቤን ነጋሽ አንዲሁም ወደ አገውና መተማ የተስፋፋዉ ይህ ኪንቺያ የሚባል የበለስ ባክቴርያ ተስፋፍቶ ተፈጥሮ እንዳይጨርስ አሁንም የሳይንስ ምሁራን የዜግነት ግዳጃችሁን ብታውቁ።

በውጭ አገር የምትገኙ ኢትዮጵያወያን ሁሉ በምስራቅ ፣ በደቡብምስራቅ በደቡብ ትግራይ ዞኖች ተፈሮ ያለዉ በበለስ እፅዋት ቫይረስ የአለም የሳይንስ ምሁራን ይምርምር እርዳታዎን እንዲለግሱ ታደርጉ ዘንድ ጥሪዬን አቀርባለሁ::

የሃገራችን የሃይማኖት መሪዎች የእድሜ ባለፀጎች የተቀዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ምሁራን ተማረሚዎች ወጣቶች ማህበራት ይህ አደጋ ለመከላከል የአቅማችሁን በመስራት ለመንግስት ተፅእኖ በማድረግ የተለመደዉ ልግስናችሁን ትችሩ ዘንድ ጥርዬን አቀርባለሁ።

ባገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ለዚህ በበለስ እፅዋትና የበለስ ተጠቃሚዎች የሆኑ ዜጎች የመኖር መብት የመኖር አቤት በቦታዉ መጥታችሁ ምስክርነታችሁን ትሰጡ ዘንድ ጥሪዬን አቀር ባለሁ። እንደዚሁ ያገር ውስጥና የውጭ እርዳታ ለጋሽ የመሆናችሁ ለዚህ ህዝብ ድረሱለት ህዝብ እየተበታተነ ነዉ።

በሃገራችን ያላችሁ የነፃ ፕሬስ ጋዜጠኞች ከያኒዎች ፀሃፊዎች አመደኞች በዚህ በተሸገረዉ ህዘብ በአካል አይታችሁ ለኢትዮጵያ ህዝብና ለአለም አስታውቁት በተጨማሪ የውጭ ብዙሃን መገናኛም ለዚህ አዲስ አ ደጋ ተከታትላችሁ ብትዘግቡት

የሃገራችን የወገን ወዳጅ የሆናችሁ ጠበቆች ለዚህ እፅዋት አውዳሚ ቫይረስ ያስገቡ ህዝቡ ለረሃብ ለስደት የዳረጉ ባለስልጣናትና ተመራማሪ ተብዬዎች ደንቆሮ ዶክተሮች ወ ደ ህግ አቅርባችሁ ታስፈርዱዋቸዉ ዘንድ ደግሜ ጥርዬን አቀርባለሁ በተለይ በቅርብ የምትመለከቱት ያላችሁ በመቐለ የምትገኙ ጠበቆች በቆራጥነት በህግ ድጋፍ ብታደርጉ ለወገን ደራሽ ወገን ነውና::

ከአንድነት ፓርቲ ኢንጂነር ግዛቸው ካቢኔ ስድስቱ አመራሮች ራሳቸውን አገለሉ።

$
0
0

UDJስድስት የአንድነት መራሮች በኣንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው የሚመራ ካቤኔ ውስጥ መቀጠላቸው ትርጉመ ቢስ መሆኑን መረዳታቸውን በመግለጽ ለግዛቸው ደብዳቤ ያስገቡት የአንድነት አመራሮች
ተክሌ በቀለ –ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት
በላይ ፈቃዱ —ምክትል ፕሬዘዳንት
ሰለሞን ስዮም —የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ
ዳንኤል ተፈራ — የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ
ዳዊት አስራደ —የኢኮኖሚ ጉዳዮች
ፀጋየ አላምረው -–የገንዘብ ክፍል ሃላፊ    ሀላፊ : ራሳቸውን ከኢንጅነር ግዛቸው ካቢኔ ማግለላቸው ታውቋል።

ኢንጂነር ግዛቸው በአንድነት እና በመኢአድ መካከል የሚደረገውን ውህደት በማኮላሸት ስራ ላይ ከመሰማራታቸውም ሌላ ሰርጎገቦችን እየሰበሰቡ ፓርቲው የሚያደርጋቸውን እንቅስቃሴዎች እያበላሹ መሆኑን አቤቱታዎች ይሰማሉ፡፤እንዲሁም በጀግናው አንዱአለም አራጌ እና በሃብታሙ መታሰር ጋር እንደሚጠረጠሩ እና የአንድነትን እንቅስቃሴ በዘለቀ ረዲ በኩል ለወያኔ ሪፖርት እንደሚያደርጉ በአባላቶቹ አቤቱታ ይቀርብባቸዋል።

Health: በቀዶ ጥገና ወቅት በሽተኛው ከሰመመን ቢነቃ ምን ሊፈጠር ይችላል?

$
0
0

የቀዶ ጥገና በሚሰራበት ወቅት የማደንዘዣ መድሃኒቶች እንደሚሰጡ አውቃለሁ፡፡ ሆኖም የእነዚህ መድሃኒቶች የአሰራር ምስጢር ምን ይሆን እያልኩ ሁሌ ራሴን እጠይቃለሁ፡፡ ለመሆኑ እንዴት ነው ሰው ሰውነቱ በስለት እየተቆራረጠ ምንም እንዳይሰማው ማድረግ የሚቻለው? በመሀል በሽተኛው ቢነቃስ ምንድነው የሚፈጠረው? እባካችሁን እስቲ በእነዚህ መድሃኒቶች ዙሪያ ማብራሪያ ስጡኝ?
ሜሮን ነኝ

ሜሮን የጠየቅሽን ጥያቄ የብዙ አንባቢዎቻችንም ጥያቄ ይመስለናል፡፡ መድሃኒቶቹ በጤናው ዘርፍ በጣም ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከቱና እያበረከቱም ያሉ ናቸው፡፡ የህክምና አብዮትን የፈጠሩ የእነዚህን ድንቅ የዘመናችን መድሃኒቶችን አሰራር ማወቅ ብዙ ፋይዳ አለው፡፡ እና ስለነዚህ መድሃኒቶች ማወቅ ጠቃሚ በመሆኑ ለአጠቃላይ ግንዛቤ ይረዳ ዘንድ እንደሚከተለው ተዳሷል፡፡
ማደንዘዣ
ብዙ አይነት የሰመመን መድሃኒቶች ሲኖሩ በአጠቃላይ ከአሰራራቸው አንፃር በሁለት ይከፈላሉ፡፡ የመጀመሪያው ለከባድ ቀዶ ህክምና የሚሰጠውና ራስን በማሳት መላ ሰውነትን የሚያደነዝዘው ሲሆን ‹‹ጀነራል አንስቴዥያ›› በመባል ይታወቃል፡፡ ሌላው ለመለስተኛ ቀዶ ህክምና የሚያገለግለው እና ህክምናው የሚሰጥበትን የአካል ክፍል ብቻ የሚያደነዝዘው ሲሆን ‹‹ሎካል አንስቴዥያ›› በመባል ይታወቃል፡፡ ይሄኛው ራስን ሙሉ በሙሉ አያስትም፡፡ የምጥ ህመምን ለመቀነስ ከወገብ በታች የሚያደነዝዘው አይነትም(ስፓይናል አንስቴዥያ) ከዚህኛው አይነት መመደብ ይቻላል፡፡
አሰጣጣቸውም በደም ስር ወይም በጡንቻ ስር በመውጋት አሊያም በጋዝ መልክ በአፍንጫ በመሳብ ሊሆን ይችላል፡፡ ዋነኛው አጠቃላይ ማደንዘዣ በሚሰጥበት ወቅት እንደየሁኔታው መድሃኒቶቹን እርስ በርሳቸው ወይም ከሌላ መድሃኒት ጋር ማጣመር ሊያስፈልግ ይችላል፡፡ በተለይ ጡንቻን ዘና በማድረግ ለህክምናው አጋዥ የሆኑ መድሃኒቶች አብረው ይሰጣሉ፡፡

ሰውነታችን በአጠቃላይ በተለይም የነርቭ ስርዓታችን ያልተለመዱና የማይመቹ ወይም ጎኒ የሆኑ ውጫዊም ሆነ ውስጣዊ ትንኮሳዎች የሚለይበትና ለዚህም አጸፋዊ የመከላከል እርምጃ የሚወስድበት የራሱ የሆነ ድንቅ ጥበብ አለው፡፡ በምሳሌ እንየው፡፡ የጋለ ምድጃን ድንገት ሳናስበው ብንነካው ፈጣኑ የነርቭ ስርዓታችን ይህ ክስተት አደገኛ መሆኑንና ቶሎ ካልተወገደ ከባድ ቃጠሎና ህመም እንደሚያስከትል ተገንዝቦ በድንገት ከቃጠሎው እጃችንን እንድናርቅ ያደርጋል፡፡ ይህ ሁሉ የሚከናወነው ታዲያ በሽርፍራፊ ሰከንዶች መሆኑ ይበልጥ ያስደንቃል፡፡ መልዕክቱ በቅጽበት ቆዳ ላይ ባሉ ህመምን በሚለዩ ህዋሶች ተለይቶ በነርቮች አማካይነት ወደ አንጎል ይደርሳል፡፡ እዚያም ተተርጉሞ ምላሹ ወደ ጡንቻዎችና መገጣጠሚያዎች በሌሎች ነርቮች አማካይነት ተመልሶ ራስን የማዳን አጸፋዊ ተግባር በቅጽበት ያከናውናል፡፡

ውድ ጠያቂያችን ሜሮን የማደንዘዣዎች አሰራርም ይህንን የነርቭ ስርዓት ሂደት መቀነስ፣ መገደብ ወይም ማስወገድ ነው፡፡ ስለሆነም ታካሚው በቀዶ ህክምናው ወቅት ምንም አሳማሚ ስሜቶች ሳይሰማው ዘና እንዲል ያስችለዋል፡፡ ያማ ባይሆን እንኳንስ ‹‹በተቀደሰው ቢላዋ›› መቆረጥ ይቅር እና ጠንከር ያለ ቁንጥጫስ ቢሆን ‹‹ዘራፍ!›› አሰኝቶ ያፈናጥረን የለ፡፡ ዕድሜ ለሰመመኑ እንጂ የህክምና ስታፍ ሁሉ ቡጢና ጡጫ በቀመሰ ነበር- በታካሚው ቅጽበታዊ እርምጃ አማካይነት ማለት ነው፡፡ በዚህ አይነት በጊዜያዊነት ራስን በማሳትና ጡንቻን በማዛል ካልተፈለገ የሰውነት ምላሽ ከመከላከልም በላይ ታካሚውን ካላስፈላጊ ስቃይና ጭንቀት ይታደጋሉ፡፡ ይህ መሰረታዊ የማደንዘዣዎች የአሰራር ሂደት ሲሆን እስካሁንም ብዙ ያልተደረሰባቸው የአሰራር ምስጢሮች እንዳሉት ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ ተመራማሪዎችም ምስጢሩን የመፈተሽ ተግባራቸውን አላቆሙም፡፡ ሳይንስ ጥበብና ቴክኖሎጂ ምን መቆሚያ አለውና፡፡

ውድ ሜሮን ስለ ሰመመን መድሃኒቶች ሲወሳ መረሳት የሌለበት ሌላው ጉዳይ መድሃኒቶችን ስለሚሰጡት ባለሙያዎች ነው፡፡ ለዚህ ሙያ በቀጥታ የሰለጠኑ ባለሙያዎች (Anaesthetists) ሲባሉ፤ ሐኪም ሆነው በተጨማሪ በሙያው ስፔሻላይዝ ያደረጉ ከሆኑ (Anaesthetologist) ይባላሉ፡፡ በቀዶ ህክምና ቡድኑ ውስጥ በህክምናው ውጤታማነት በተለይም ማደንዘዣው የታሰበለትን ግብ እንዲመታ ከማስቻል አንፃር የእነዚህ ባለሙያዎች አስተዋፅኦ ላቅ ያለ ነው፡፡
ዋነኛ ተግባራቸውም ከዋናው ቀዶ ህክምና በፊት ይጀምራል፡፡ ይኸውም ከታካሚው፣ አሳካሚዎቹና ከሌሎች የጤና ባለሙያዎች ጋር በመተባበር በሽተኛው የሰመመን መድሃኒቱንና ቀዶ ህክምናውን መቋቋም የሚችል ትክክለኛ ዕጩ ስለመሆን አለመሆኑ፤ ይህን አስቸጋሪ የሚያደርጉ ተጓዳኝ በሽታዎች ከፍተኛ ደም ግፊት፣ ስኳር፣ ደም ማነስ… መኖር አለመኖራቸው የመድሃኒቶች ‹‹አለርጂ›› ስለመኖር አለመኖሩ እንዲሁም ቀድሞ መደረግ ስለሚገባቸው ሌሎች ቅድመ ዝግጅቶች ወዘተ በማጣራት አስፈላጊውን ውሳኔና እርምጃ ይወስዳሉ፡፡ በቀዶ ህክምናው ወቅትም መድሃኒቶቹን መጥኖ ከመስጠት ባለፈም የበሽታውን ደም ግፊት፣ የልብ ምት፣ የአንጎልና የነርቮች ሁኔታና ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀ መቆጣጠሪያ መሳሪያ አማካኝነት ይከታተላሉ፡፡ ጊዜአዊ የመተንፈሻ ቱቦ ማስገባትና በመጨረሻም ማስወጣትም ሌላው ተግባራቸው ነው፡፡ በመጨረሻም ታካሚው ሙሉ በሙሉ ከማደንዘዣው ተፅዕኖ መላቀቁንና መንቃቱን በማረጋገጥ ተግባራቸውን ያገባድዳሉ፡፡

በነገራችን ላይ የግድ መውሰድ ካለባቸው መድሃኒቶች በስተቀር ከባድ ቀዶ ህክምና የሚደረግለት በሽተኛ ቢያንስ ከህክምናው በፊት ከ6-12 ሰዓታት ምንም አይነት ምግብም ፈሳሽ መጠጥም መውሰድ አይፈቀድለትም፡፡

የማደንዘዣ መድሃኒቶችና አንፃራዊ ጉዳታቸው

የማደንዘዣ መድሃኒቶችም እንደማንኛውም መድሃኒት አንፃራዊ የጎን ጉዳት አላቸው፡፡ ጉዳቶቹም ከቀላል ጀምሮ ህይወትን ሊያሳጣ እስከሚችል ከባድ ጉዳት ይለያያል፡፡ ለምሳሌ ከባድ አለርጂክ ሪያክሽን፡፡ ከበድ ያሉት ችግሮች ያልተለመዱና ከስንት አንዴ የሚከሰቱ ሲሆኑ ብዙዎቹ በቅድመ ጥንቃቄና ክትትል ሊወገዱ ይችላሉ፡፡ ዋነኞቹ የጎን ጉዳቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡ ማቅለሽለሽ፣ ማንቀጥቀጥ፣ የጉሮሮ ቁስለትና ህመም፣ የነርቭ መደንዘዝ፣ ቶሎ አለመንቃት… የመሳሰሉት ናቸው፡፡ ለምሳ በምሉ በመድሃኒቶቹ ሳቢያ የሚከሰት ሞት ከ200 ሺ ሰዎች በአንዱ ብቻ ነው፡፡ ሆኖም ግን ደም ግፊት ወይም ልብ ድካም የመሳሰሉ ተጓዳኝ በሽታዎች ባለባቸው ታካሚዎች ላይ የሞት አደጋው ከአንድ እስከ ሁለት በመቶ ከፍ ሊል ይችላል፡፡
ሌላው አልፎ አልፎ ሊከሰት የሚችለው ችግር በሰመመን ውስጥ ሆነውም የህመም ስሜት መሰማቱ ነው፡፡ በዚህ አይነት የተወሰኑ ታካሚዎች ላላስፈላጊ ህመም ሊጋለጡ እንደሚችሉ በቅርቡ ቢቢሲ ያወጣው መረጃ ይጠቁማል፡፡ ፀረ-ህመም መድሃኒቶችን በመጠቀምና በሌሎችም ቅድመ ህክምናዎች (premediatations) እንዲህ አይነቱን ህመም መቀነስ ወይም ማስወገድ ይቻላል፡፡ የመስኩ ተመራማሪዎችም ለእንዲህ አይነቱ ህመም መንስኤና መፍትሄ ፍለጋ በመትጋት ላይ ናቸው፡፡ ምክንያቱም ህክም ከህመምና ከስቃይ የፀዳ መሆን ስላለበት፡፡
ውድ ጠያቂያችን ሌላው ይበልጥ አስገራሚውና አሳሳቢው ጉዳይ በማደንዘዣ ውስጥም ሆኖ ንቁ መሆን (Anesthesia awareness) ነው፡፡ ይህ ያልተለመደ ቢሆንም ሁኔታው አስፈሪና አሳሳቢ ነው፡፡

በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 65 ላይ ታትሞ የወጣ።

(ሰበር ዜና) ፍትህ ሚ/ር የክስ ቻርጆችን ለሃገር ቤት ጋዜጠኞች ማደል ጀመረ (የሎሚ መጽሔትን የክስ ቻርጅ ይዘናል)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ቀድሞ በኢትዮጵያ ያሉትን መጽሔቶችን እና ጋዜጦችን እንደሚከስ ያስታወቀው የሕወሓት አስተዳደር ፍትህ ሚ/ር ለጋዜጠኞች የክስ ቻርጆችን ማደል ጀመረ። በዛሬው ዕለት የሎሚ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ እና ድርጅቱ ዳዲስሞስ ኢንተርቴይመንትና የፕሬስ ሥራዎች ኃ/የተ/የግል ማህበር የክስ ቻርጅ እንደደረሰው ለዘ-ሐበሻ የመጣው መረጃ አመለከተ።

ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ

ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ


በተመሳሳይ እንደሚከሰሱ የተነገራቸው የአዲስ ጉዳይ ጋዜጠኞች ሃገር ጥለው ለመሰደድ የበቁ መሆኑን ዘ-ሐበሻ በትናንትናው ዕለት መዘገቧ ይታወሳል።

በሎሚ መጽሔት አዘጋጅ ላይ የሕወሓት አስተዳደር ፍትህ ሚ/ር ያቀረበው ክስ “ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ወንጀሉና ወንጀሉ የሚሰጠውን ውጤት በመቀበል መንግስት የሚለወጠው ህገ መንግስታዊ በሆነ መርህ በምርጫ ሆኖ እያለ ኢ-ህገመንግስታዊ በሆነ መንገድ በአመጽ ሥርዓቱን ለመጣል” የሚል ሲሆን ለክስ ያበቁት ጽሁፎችም
1ኛ. በሎሚ መጽሄት ቅጽ 3 ቁጥር 109 “በዓለም በጨቋኝነቷ አቻ የማይገኝላት የሚዲያ ምህዳር በኢትዮጵያ” የሚለው
2ኛ. ሰብ አዊ መብት የሚባል በኢትዮጵያ መንግስት ሙሉ በሙሉ ተረስቷል። የምንገኝበትም ዓለም በመራጮችና የለውጥ ማዕበሎች የሰፈነበት በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በቀጣይ ዓመት በሚደረገው የአገራዊ አጠቃላይ ምርጫ በመንተራስ ለበርካታ ዓመታት ከዘለቀ የፍ የጭቆና አገዛዝ ለመላከክ የማይቀረውን የለውጥ ማዕበል ለማምጣት እራሳቸውን ለተጠናከረ ሕዝባዊ ዓመጽ ማደራጀት መጀመራቸው ሊበረታታ የሚገባው ነው” በሚል አረፍተ ነገር፤
3ኛ. በሎሚ ቁጥር 91 ላይ “የአሸባሪነት ፈርጦች” በሚል ር ዕስት ‘ኢህ አዴግም ከማን አንሼ በሚል ስሜት ተቃራኒ ሃሳብ የሚያቀርቡ ጋዜጠኞችን ለስልጣኔ/ወንበሬ) ያስገኛል የሚላቸውን ጠንካራ ተቃዋሚዎችን እያደነ በአሸባሪነት ስም ወህኒ ያወርዳቸው ከጀመረ ሰንብቷል በሚል ጽፏል በሚል
4ኛ.”የኢሕአዴግ የሽብርተኝነት መመዘኛ ምንድን ነው?” “ኢህአዴግ” የሕዝብ ተቀባይነት ያገኘ አይመስለውም ሕዝብ የተቀበለውና አምነዋለው የሚለው ሰው ለኢህ አዴግ ጠላት ነው፤ ሽብርተኛ ተብሎ ይከሰሳል በማለት በሽብር ህግ ተከሰው የተቀጡ ተከሳሾች በህዝብ የሚወደዱና ለገዢ ፓርቲ ተቀናቃኝ በመሆናቸው ብቻ በግፍ የተቀጡ ንጹሃን እንደሆኑ የሚያስመስል ጽሑፍ አቅርቧል በሚል 4 ክሶች ቀርበውበታል።

የክስ ቻርጆቹን ተመልከቷቸው፤ ተጨማሪ መረጃዎች እንደደርሱን እንመለሳለን።
feteh Lomi 1

feteh Lomi 2

feteh Lomi 3

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live