Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ወይ አዲስ አበባ፤ አዲሱ ገንዝብ ማግኛ ሥራ ውሃን አዝሎ ማሳለፍ 3 ብር ብቻ (ቪድዮ)

0
0

ይህ ቪድዮ የሚያሳየን አዲስ አበባ በጎርፍ ተጥለጥልቃ ነው። ሕዝቡ ትንሿን ጎርፍ ታዝሎ ለማለፍ 3 ብር ይከፍላል። ቻይና የሰራው መንገድ ቻይና ለሰራው ጫማ ጠንቅ ስለሆነ ሕዝቡ ከቻይና የገዛ ጫማ እንዳይበላሽ በቻይና ጫማ መግዣ ባነሳ ዋጋ ታዝሎ ውሃውን ይሻገራል። ቪዲውዮው ያለውን ይናገራል፤ ይመልከቱት።

ወይ አዲስ አበባ፤ አዲሱ ገንዝብ ማግኛ ሥራ ውሃን አዝሎ ማሳለፍ (ቪድዮ)


በ5 ዋነኛ መጽሔቶች እና አንድ ጋዜጣ ላይ የወንጀል ክስ ተመሠረተ

0
0

በስድስት የግል ፕሬስ ሕትመቶች እና አሳታሚዎቻቸው ላይ የወንጀል ክስ መመሥረቱን መንግስት አስታወቀ፡፡

ክስ የተመሠረተባቸው አምስት መጽሔቶች እና አንድ ጋዜጣ፤ በየጊዜው ህገ መንግስቱንና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በሀይል ለመናድ የአመፅ ቅስቀሳና የሀሰት ወሬዎችን በመንዛት ህገ መንግስታዊ ስርዓቱ በሀይል እንዲፈረስ እና ህዝብ በመንግስት ላይ ያለአግባብ አመኔታ እንዲያጣ የሚያደርጉ የወንጀል ተግባራትን በመፈፀም እንደተጠረጠሩ የፍትህ ሚኒስቴር መግለጫ ጠቁሟል፡፡Lomi-magazine-

መግለጫው አክሎ በጥቅሉ ባቀረበው ስሞታ፤ በህገ መንግስቱ የተበጁትን ገደቦች በማን አለበኝነት በመጣስ ስራዬ ብለው ብሄራዊ ደህንነትን አደጋ ላይ በሚጥል መልክ አመፅና ሁከትን የሚቀሰቅሱ፣ አክራሪነትንና ሽብርተኝነትን የሚያወድሱ እንዲሁም የሚያበረታቱ፣ በህዝቡ መሃከል የዘርና የሃይማኖት ጥላቻን የሚቀሰቅሱ፣ የህዝብ መሪዎችንና የተቋማትን መልካም ስምና ዝና በሀሰት የሚያጠፉና የሚወነጅሉ፤ የግል ሕትመት ውጤቶች አሉ ብሏል፡፡

ክስ የተመሠረተባቸው የሕትመት ውጤቶች፡-

* አዲስ ጉዳይ – በሮዝ አሳታሚ ኃ.የተ.የግ.ማህበር አሳታሚነት የሚታተም – ሳምንታዊ መጽሄት፣

* ሎሚ መጽሄት – በዳዲሞስ ኢንተርቴንመንትና እና ፕሬስ ስራዎች ኃ/የተ/የግ/ማ አሳታሚነት የሚታተም – ሳምንታዊ መጽሄት፣

* ዕንቁ መጽሄት – በአለማየሁ ሕትመትና ማስታወቂያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር አሳታሚነት – በየ15 ቀኑ የሚታተም መጽሄት፣

* ፋክት መጽሄት – በዮፋ ኢንተርቴንመንትና ፕሬስ ስራዎች ኃ.የተ.የግ.ማህበር አሳታሚነት የሚታተም – ሳምንታዊ መጽሄት፣

* ጃኖ መጽሄት በአስናቀ ኢንተርቴይመንትና ፕሬስ ሥራዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበር አሳታሚነት – በየ15 ቀኑ የሚታተም መጽሄት፣ እና

* በቅርብ ወደ ሕትመት የገባው አፍሮ-ታይምስ ጋዜጣ (የሎሚ መጽሔት እህት እንደሆነ የሚታመን) ናቸው፡፡

እንደ ፍትህ ሚኒስቴር መግለጫ፤ ክስ የመመሥረት ውሳኔ የተወሰደው ህትመቶቹ ‹‹ምግባራቸውን እንዲያርቁ›› ሌሎች አማራጮች አሟጦ በመጠቀም ያላሰለሰ ጥረት ከተደረገ በኋላ፤ እንዲሁም ‹‹የጥቃታቸው ሰለባ የሆነው ህዝብም በእነዚህ የህትመት ውጤቶች የህግ ከለላ በተሰጣቸው ጥቅሞቹ ላይ ያለማቋረጥ የሚደርሰውን ጥሰት ለማስቆም መንግስት ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድ በተለያዩ መንገዶች›› በመጠየቁ ነው ብሏል፡፡እንደመግለጫው ከሆነ፤ ክስ የማቅረቡ ሂደትም ‹‹በማን አለብኝነት በተደጋጋሚ ህጉን በጣሱ እና በሚጥሱ አሳታሚዎችና የመገናኛ ብዙሃን ድርጅቶች ላይ›› ይቀጥላል፡፡

አምስቱ መጽሔቶች በሽያጭ ብዛታቸው በመጀመሪያ ረድፍ የሚሰለፉ አንደሆኑ ሆርን አፌይርስ ከጥቂት ወራት በፊት ከብሮድካስቲንግ ባስልጣን ያገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡

መጽሔቶቹ፤ ባለፈው ጥር በመንግስት በተሠራው ‹‹በሰባት መጽሄቶች በተከታታይ ህትመቶቻቸው በአሉታና በተደጋጋሚ ያነሷቸው ጉዳዮች የአዝማሚያ ትንተና›› የተሰኘ ጥናት ውስጥ የተካተቱ መሆናቸው ይታወሳል፡፡

Source-hornaffairs

የመኢአድና የአንድነት ውህደት በምርጫ ቦርድ ለማጨናገፍ የሚደረገውን ሴራ አስመልክቶ ዛሬ በመኢአድ ጽ/ቤት መግለጫ ሰጡ

0
0

ፍኖተ ነፃነት

መኢአድና አንድነት ወደ ሰላማዊ የትግል ፍልሚያ ውስጥ መግባታቸውን ለሕዝባቸው ማሳወቅ ይወዳሉ

10386311
መኢአድና አንድነት በዛሬው ዕለት ውህደቱን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ በህወሓት/ኢህአዴግ አባላት የሚመራው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በበሰላማዊ ትግሉ ላይ መሰናክሎችን በመፍጠር ካሁን ቀደም የተደረጉ ምርጫዎች እንዲዘረፉና ኮሮጆ እየተገለበጠ ለገዢው ፓርቲ እንዲሰጥ ከፍተኛ ሚና ሲጫወት መቆየቱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ እንደሆነ ገልጸው በየክልሉ፣ በየዞኑና ወረዳዎች የተሰማሩ የምርጫ ቦርድ ኃላፊዎች የገዢው ፓርቲ የካቢኔ አባላት፣ የደህንነት አባላት መሆናቸው የማይካድ ሃቅ መሆኑ ግልጽ ቢሆንም ዛሬ በግልጽ እንዳይዋሃዱ የሚደረገው ስውር ደባና ፓርቲዎችን ለመዝጋት የሚደረገው ሙከራ ማድረጉና የነፃው ፕሬስ በመዝጋት የኢትዮጵያ ሕዝብ አማራጭ እንዲያጣ የሚፈጸመው ድርጊት ከድፍረቶች ሁሉ ድፍረት ነው ሲሉ በመግለጫቸው ገልጸዋል፡፡ በመጨረሻም የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ከሕዝብ የተጣለበትን ከባድ ኃላፊነት ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ከያዘው የጥፋት መስመር በመመለስ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎችንና ሕዝባችንን በትክክለኛው መንገድ እንዲያገለግል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን በማለት መግለጫቸውን አጠቃለዋል ፡

10486455

101

1051 1054 10

 

 

መብራት የለም በሚል ሰበብ የኢትዮጵያ ሙስሊም መሪዎች ችሎት ሳይደረግ ቀረ፤ “የሌለው መብራት ሳይሆን ፍትህ ነው”–ታዛቢዎች

0
0

ድምጻችን ይሰማ እንደዘገበው፦

‹‹የሌለው መብራት ሳይሆን ፍትህ ነው!›› አስተያየት ሰጪዎች
ሐሙስ ነሃሴ 1/2006

muslimከትናንት ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው የብርቅዬ ጀግኖቻችን ችሎት በዛረው እለት ሳይካሄድ ቀርቷል፡፡ ምንም እንኳን ችሎቱን ለመታደም በቦታው የተገኘው እና መሪዎቹ ሲወጡና ሲገቡ ፍቅሩን በሰላምታ ሲገልጽ የነበረው በርካታ ሙስሊም በሰዓቱ የተገኘ ቢሆንም አርፍደው የተገኙት የችሎቱ ዳኞች ዛሬ ችሎት እንደማይኖር በመንገር ለዚህም ሰበቡ ‹‹መብራት አለመኖሩ›› መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አንድ የመንግስት መስሪያ ቤት እንዲህ በተደጋጋሚ ‹‹መብራት የለም›› በሚል የሐሰት ሰበብ ችሎት ማቋረጡ እጅግ አሳፋሪ መሆኑ ሳያንስ ህንጻው ላይ ጄኔሬተር እያለም እንኳ ‹‹ጄኔሬተሩ አራተኛ ፎቅ ላይ አይደርስም›› የሚል ሰበብ መስጠታቸው የፍትህ ስርዓቱ ከደዌው የመፈወስ እድሉ አነስተኛ መሆኑን ያሳየ ከመሆን አያልፍም፡፡

በመጨረሻም ዳኞቹ የምስክርነት ማሰማት ሂደቱ ነገ አርብ እንደሚቀጥል መጀመሪያ ገልጸው የነበረ ቢሆንም መጨረሻ ላይ ግን ሃሳባቸውን በመለወጥ ለፊታችን ማክሰኞ ነሃሴ 6 የችሎት ቀጠሮ አስተላልፈው ችሎቱን አጠናቀዋል፡፡

ምንም እንኳን በህግ ሊቃውንት ሳይሆን በደህንነት እና የጸጥታ አካላት ፊሽካ ነፊነት የሚሾፈረው የፍትህ ስርዓት ለከፍተኛ ህዝባዊ ትዝብት መጋለጡ እና ዜጎች ቦታ እየነፈጉት መምጣታቸው ለመንግስት ግድ እየሰጠው ባይመስልም የፍትህ ስርአቱ ግን የማስፈጸም አቅሙ ከቀን ወደቀን እየሰለለ ሄዷል፡፡ ዓይኖቹን የዛሬ ክስተት ላይ ብቻ የተከለና አርቆ ማሰብ የተሳነው አካል ነገን ማየት ባይችልም አንገቷ ታንቆ እያጣጣረች ያለችው ፍትህ ነጻ የምትወጣበት ቀን ግን መምጣቱ፣ ግፈኞችም የእጃቸውን ማግኘታቸው ግን አይቀሬ መሆኑን የቅርብም ሆነ የሩቅ የሰው ልጆች ታሪክ ያስተምረናል፡፡ ቀጠሮ በማራዘም ንጹሃን የህዝብ ጀግኖችን መልካም ዝና ማጠልሸትም ሆነ በህዝብ ዓይን ‹‹አሸባሪ›› ማድረግም ሊሳካ የማይችል ከንቱ ሕልም ነው!

ንጹሃንን በማጉላላት የፍትህ ስርዓቱን መሸርሸር ይብቃ!!!
ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

የመለስ “ትሩፋቶች”–መጽሃፍ ቅኝት (ከጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ)

0
0

meles book
ደራሲ፣ ኤርምያስ ለገሰ
ብዛት፣ 406 ገጾች
አሳታሚ፣ ነጻነት አሳታሚ ድርጅት

እንደ መንደርደርያ
በስፋት ሲወራለት የነበረውን ይህን መጽሃፍ ሙኒክ-ጀርመን ላይ ገዝቼ ለማንበብ እያፈላለግኩ ሳለሁ፤ አንድ ወዳጄ ይዞት አየሁ። የደበዘዘ የመለስ ፎቶ ያለበትን ይህንን መጽሃፍ የኦስሎው አበበ እጅ ላይ ነበር። ገና ሰላምታ ሳንለዋወጥ ነበር መጽሃፉን ከእጁ ላይ የነጠቅኩት። ታማኝ በየነም እዚያው አብሮን ስለነበር አስተያየቱን ጣል አደረገ። “መነበብ ያለበት መጽሃፍ” እንደሆነ አበክሮ ነገረኝ። ታማኝ ኢትዮጵያን የሚመለከቱ መጻህፍት በሙሉ እንደማያመልጡት አውቃለሁ። በዚህ አዲስ መጽሃፍ ላይ አንዳች አዲስ ነገር እንደሚኖር ከንግግሩ ለመረዳት አያዳግትም።
የመጽሃፉ መታተም ወሬ እንደተሰማ በደራሲው በአቶ ኤርምያስ ለገሰ ላይ የድጋፍና የተቀውሞ ድምጾች ከሁለት ጫፎች ይሰሙ እንደነበር አስተውያለሁ። ሁለቱም ጫፎች ለክርክራቸው የየራሳቸው መከራከርያ ነጥቦች ቢኖራቸውም መደምደሚያቸው አንዱ-ካንዱ ሚዛን የሚደፉ ሆነው አላገኘኋቸሁም። ማየት የሚገባን የጫነውን ሳይሆን ጭነቱን ነው እንዲሉ፣ መልዕክተኛውን ሳይሆን ይልቁንም መልዕክቱን አንብቦ የራስ ፍርድ መስጠቱ የሚመረጥ ይሆናል። ማንበብ ከጉዳቱ ጥቅሙ ነው የሚያመዝን። መረጃ ሁሉ አይናቅም። የብዙዎቻችን ችግር ከታማኞቻቸን የምናገኘውን መረጃ ብቻ ይዘን በዚያ ቁንጽል መረጃ ተንተርሰን ውሳኔ ለመስጠት መሞከራችን ይመስለኛል። ያ ስውዬ እንዳለው ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል። የኮ/ል መንግስቱን፣ የሻምበል ፍቅረስላሴን እንዲሁም የበረከት ስማዖንን መጽሃፍትስ ገዝተን አንብበን የለ? እንደዚህ አይነቶቹ መጻህፍቶች ሙሉ ሰው እንኳ ባያደርጉን ሚዛናዊ እንድንሆን ይረዱናል።
***
መጽሃፉ ሲገለጥ
በንዑስ ርዕስ “ባለቤት አልባ ከተማ” ተብሎ የተሰየመውን “የመለስ ‘ትሮፋቶች’” እነሆ አነበብኩት..
ደራሲው፣ ኤርምያስ ለገሰ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሂሳብ ትምህርት የባችለር ዲግሪውን እንደያዘ መከላከያ ሚ/ር ውስጥ ተቀጥሮ ዝዋይ በሚገኘው የመከላከያ ኮሌጅ ከፍተኛ መኮንኖችን ለማሰልጠን ተጓዘ። በካምፑ ያሉ አብዛኞቹ መኮንኖች ከአምስትኛ ክፍል ያልዘለሉ እንደሆኑም በገጽ 209 ያስነብበናል። ወጣቱ ካድሬ እነዚያን መሃይም መኮንኖች የተፈጥሮ ሳይንስ ሊያስተምራቸው እንዳልሄደ ግልጽ ነው። ከጳጳሱ በላይ ካቶሊክ… እንዲሉ ከበረሃ የመጡ ነባር ታጋዮችን የድል አጥቢያው ካድሬ የራሳቸውን ርዕዮተ-አለም ሊለቅባቸው መሄዱ ደግሞ የበለጠ ግርታ ይፈጥራል።
ደራሲው የአብዮታዊ ዲሞክራሲን ወንጌል የተቀበለው የአራት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ነበር። እዚያ በተማሪ ስም ተመድቦ የሚሰራ ሰላይ ካድሬ ይህንን የቅጥፈት ፍልስፍና ሰብኮ እንዳጠመቀው በገጽ 192 ላይ አስፍሯል። በአራት ኪሎ ቆይታው ከሂሳብ ትምህርቱ ጎን ለጎን ቀዩዋን መጽሃፍ ሲበላት ከርሞ ኖሮ፤ የህወሃት ሃዋርያ ሆኖ እነሆ ወንጌሉን ሊሰብክ ተሰማርቷል።
ይህንን ለማድረግ ታድያ አብዮታዊ ዲሞክራሲን በስሱ ሳይሆን እስከ አንገቱ ድረስ መጋት ይኖርበታል። የድርጅቱ አይነተኛ ርእዮተ-አለም የሆነውን የባንቱስታን የክልል አገዛዝ እና የዘር ፖለቲካን አቡክቶ ማብሰል ይጠበቅበታል። ከፍ ሲል ደግሞ ኢህአዴግኛ ቋንቋ መናገር የግድ ይሆንበታል – መስፈርቱን ለሟሟላት። በገጽ 327 ላይ አብዮታዊ ዲሞክራሲን ቀጥ አድርጎ ሰላቆመው ምሰሶ ሲገልጽ፤ “በራስ ያላመኑበትን ነገር መናገር – ለህሊና የሚከብድ” ብሎታል። አለፍ በሎም እንደ ሂትለሩ ጎብልስ ውሸትን እየደጋገሙ ህዝብን ለማሳመን መሞከር (ገጽ 389) እንደሆነ ይነግረናል።
ወትሮውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ወደ ኢህአዴግ ጎራ የሚገባ ተማሪ በማህበራዊ ኑሮው ላይ ምን ያህል አደጋ እንደሚጋረጥበት በውስጡ ያለፍነው የምናውቀው ጉዳይ ነው። አንድ ተማሪ ኢህአዴግ አባል ከሆነ መጀመርያ ከህብረተሰቡ ጋር ይራራቃል። ከዚያ ከመርህ ጋር ይጋጫል። በመጨረሻም ከራሱ ጋር ይጣላል።
ኤርምያስ ያውም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆኖ ለኢህአዴግ በካድሬነት የመጠመቁ ስሜት ከምን ሊመጣ እንደቻለ ለማወቅ ያጓጓል። በመጽሃፉ ውስጥ ይህቺን ጉዳይ እንደዋዛ ሳይጠቅሳት አልፏል። በአብዮታዊ ዲሞክራሲ፣ አንድ እና አንድ ሶስት ነው የሚሆነው። እንደሁኔታው አራትም አምስትም ሊሆን ይችላል።
ወጣቱ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ካድሬ መሆን ደግሞ በሂሳብ ትምህርት አንድ ሲደመር አንድ ሁለት ነው የሚለውን ስሌት ለድርድር ማቅረብ ግድ ይለዋል። እዚያ መርህ እና እውነት የሚባል ነገር አይሰራም። ይህንን ደግሞ ኤርምያስ ራሱ በመጽሃፉ ውስጥ ባነሳቸው ርዕሶች ሁሉ ያረጋግጥልናል። “ከኢህአዴግ ጋር ያቆራረጠኝ ከራሴም ጋር ቅራኔ ውስጥ የዘፈቀኝ ሕግ ይህ ነበር።” (ገጽ 1) ሲል “እውነት የተደጋገመ ኩሸት ነው” የሚለውን የድርጅቱን የመጀመርያ ህግ ያነሳል። ህጉን በትክክል ገልጾታል።
ልዩነቱ ኤርምያስ የባነነው ከ12 አዓመታት በኋላ መሆኑ ነው። በነዚያ አመታት ከተራ ካድሬነት አልፎ ልዩ-ልዩ ሃላፊነትን ተሸክሞ በሰባራው ሃዲድ ረጅም ተጉዟል። ከአዲስ አበባ የምክር ቤት አባልነት እስከ መንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዴኤታ የሚደርስ የስልጣን ተሸክሟል። በመጽሃፉ የዘረዘራቸው ዘግናኝ ዝርፊያዎች ሲካሄዱ አይንና ጆሮውን ከልሎት የነበረው ይህ ሸክም ይሆን? በገጽ 303 ላይ “እኔ ኢሕአዴግ ነበርኩ። ያውም እውነቱ እስኪገለጥልኝ በእምነት የምተጋ ካድሬ። ….10ሺ የሚጠጉ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በአብዮታዊ ዲሞክራሲ እያጠመቅኩ ኢሕአዴግ አርገያለሁ።” ብሎናላ!
***
መጽሃፉ በስምንት ክፍሎች ተመድቦ በሃያ አምስት ምዕራፎች ተሸንሽኗል። በዋናነት ግን በሶስት ጉዳዮች ላይ እያጠነጠነ በዚህ ዙርያ ተዛማች የሆኑ መረጃዎችን ያስነብበናል። በአንዲት ጀምበር ቢሊየነር የሚያደርገው የባለቤት አልባዋ አዲስ አበባ የመሬት ዘረፋና የምርጫ 92/97/2000 እንድምታዎችን በግንባር ቀደምትነት ይተነትናል። እንዲሁም የባድመ ጦርነት አስከትሎ ያመጣቸውን መዘዞችን በስሱ ለመዳሰስ ሞክሯል።
የጨለማውን አሊ አብዶ ዘመን በግርድፉ ይዳስሳል። የካዛንችሱ ስውር መንግስት አሊ አብዶን በርቀት እንዴት ይነዳው እንደነበር ያወሳል። የበለጠ ትኩረቱ ግን በአርከበ እቁባይ አስተዳድር ችግሮች ላይ ነው። በነዚህ ዘመናት ዘረፋው ግዙፍ፣ ችግሮቹም ውስብስብ ነበሩ። በእውነት ለመናገር በመጽሃፉ የተነሱት በደሎች እና ዘረፋዎች የአደባባይ ምስጢሮች ናቸው። አብዛኞቹ ከግሉ መገናኛ ብዙሃን የተደበቁ አልነበሩም። ይህ መጽሃፍ ዝርፍያዎቹ መቼ፣ እንዴት እና በማን ተፈጸሙ ለሚሉት ጥያቄዎች ምላሽ እየሰጠ የቀድሞዎቹን መረጃዎች የተሟላ ያደርጋቸዋል። ጉዳዮቹን በስፋት እና በጥልቀት ለማወቅ የሚያስችል ግንዛቤም ይሰጠናል። ከንቲባ አሊ አብዶ ዘመን ሁላቱን ታላላቅ እምነቶች ለማጋጨት እሳቤ ሆኖ፣ በታቦት ማረፍያዎች ሳይቀር መስጊድ እንዲሰሩበት ይደረግ እንደነበር ቀደም ብሎ ተዘግቧል። አርከበ እቁባይ ከንቲባ ሆኖ ሲሾም የካቢኔ አባለቱን ከትግራይ ጭኖ ባመጠቸው መሃይማን ካድሬዎች መሙላቱም አዲስ መረጃ አይደለም። የጠገበው ጅብ ሲሄድ የራበው መተካቱን የማያውቅ የለም። የኤርምያስ መጽሃፍ ግን መረጃውን በማስረጃ እየደገፈ ይተርክልናል። ለተራው አንባቢ ትርጉም ባይሰጥም፤ የበርካታ ሹማምንት ስሞችን በመጽሃፉ ተደርድረው እናገኛለን።
የመለስ “ትሮፋቶች” ደረቅ የፖለቲካ ትንተና ላይ የሚያተኩር ያለመሆኑ መጽሃፉን ያለትንፋሽ እንዲነበብ ያደርገዋል። በአንድ ጎኑ ጥርስ የማያስከድኑ፤ በሌላ በኩል ደግሞ አንጀት የሚያቃጥሉ እውነታዎችን ይዟል።

ተወርቶ የማያልቀው የአርከበ እቁባይ ታሪክ ውስጥ የካድሬ ተስፋ ብርሃን ጉዳይ ሰፍሯል። ተስፋ ብርሃን መስማት የተሳነው ህመምተኛ ነው። አርከበ ከመቀሌ አስጭኖ ያስመጣው ካድሬ። ሲቪል ሰርቪሱን፤ ትምህርት ቢሮን እና አጠቃላይ አቅም ግንባታውን እንዲመራ ሃላፊነት ተሰጥቶታል። ገብረተንሳይ የሚባለው ሌላኛው ካድሬ በአንድ ግምገማ ላይ “አንተ ደንቆሮ ነህ። ካንተ ጋር እንዴት እንደምሰራ አይገባኝም?” ይለዋል። መስማት የተሳነው ተስፋብርሃን መልሶ “ገብረተንሳይ ልክ ነው የመምህራን ስልጠና መስጠት አለብን።” አለው (የመለስ “ትሮፋቶች” ገጽ 132)። ደራሲው በየግምገማዎቹ ይከሰቱ የነበሩ እንደነዚህ አይነት ጥርስ የማያስከድኑ ትውስታዎችን በመጽሃፉ ውስጥ አስፍሯቸዋል። በተላይ የካድሬ ጨነቀ ታሪክ (ገጽ 150-155) ‘ጧ ‘ አድርጎ ከማሳቁ ባሻገር ስርዓቱ በሕዝብ ላይ ምን ያህል እየቀለደ እንደሆነ ያሳየናል።
በገጽ 224-225 የሰፈረው የአቦይ ስብሃት ጉዳይም ጥርስ በጣም ያስቃል።
ጸሃፊው በአብዛኛው ርእሶቹ እንደመነሻ የሚያደርገው የበረከት ስምዖንን “የሁለት ምርጫዎች ወግ” እንደሰበዝ የሚመዘዙ ስንኞች በመጠቃቀስ ነው። በአንባቢያን ዘንድ ብዝም ትኩረት ያልሳበው የበረከትን መጽሃፍ በውሽት የታጨቁ ድርሰቶች አድርጎ ለማቅረብ ሞክሯል። በከፊል በማስረጃ እያስደገፈ ነው ድርሰቱን ያጣጣለው። የበረከትን “የሁለት ምርጫዎች ወግ” ያላነበበ ካለ ዋና ዋናዎቹን የበረከት መርዘኛ መልዕክቶች ከነማፍረሻቸው በዚህ መጽሃፍ ውስጥ ያገኛቸዋል። ኤርምያስ አብዮታዊ ዲሞክራሲን በበረሃ ከተጠመቁት የህወሃት ካድሬዎች ጋር እኩል ቀርቦ ከማእዱ ሊቋደስ ከቶውን እንደማይችል እርግጥ ነው። በዚያ ላይ ከቅዱሰ-ቅዱሳኑ ለመግባት የዘር መስፈርቱን አያሟላም። እንደማንኛውም የድል አጥብያ ካድሬ በታማኝነቱ መጠን እነ በረከት እውቀቱን ተጠቅመውባታል። በሃገሪቷ ወሳኝ ጉዳዮችና ውሳኔዎች ላይ የመጀመርያ መረጃ ሊኖረው እንደማይችል ግልጽ ነው። ከመጽሃፉ እንዳየነው አብዛኞቹን መከራከርያ ነጥቦቹ የሚያተኩሩት ከየግምገማዎቹ ባገኛቸው መረጃዎች ላይ ነው። በምኒስትር ዴኤታ ማዕረግ ላይ ያለ ሰው ማወቅ የሚገባውን እንኳን አያውቅም። ለምሳሌ በገጽ 376 ላይ በኢትዮ-ኤርትራና ኢትዮ-ሶማልያ ጦርነት ክ120ሺህ የሃገራችን ወጣቶች ማለቃቸውን በይፋ የሰማው በአንድ ግምገማ ላይ ከወ/ሮ አዜብ መሆኑን ይናገራል።
በመጽሃፉ አልፎ አልፎ በቅንፍ የቀረቡ መረጃዎች ውስጥ፤ የሃይሌ ገ/ስላሴ አድርባይነት፣ የቴዲ አፍሮ በአዜብ ጥርስ ውስጥ መግባት እና ጉዳዩን ይዞ የነበረው ካድሬ ዳኛ ልዑል፣ የፕ/ር መረራና ዶ/ር በየነ ጉዳይ የሚያስደምሙ ናቸው። “ጉራጌ መራሽ አብዮት” ያሉትን ነቅናቄ ለመቀልበስ በተከወነው ሴራ (ገጽ 232-234) ታታሪውን የጉራጌ ህዝብ ዛሬ ከጫወታ ውጭ እንዳደረገው ይገልጻል።
የአያት መኖርያ ቤት ድርጅትን (ሪል ስቴት) ሙስና ለመታደግ፤ እነ በረከት ስምዖን የግሉን ፕሬስ ሳይቀር በማሳተፍ የሰሩት ድራማ (ገጽ 326) ለአንባቢው አዲስ ነገር ነው። የዚህ መጽሃፍ ደራሲ፣ ኤርምያስ ለገሰ በዚህ “አሳዛኝ” በሚለው ጥፋት ላይ መሳተፉን በጸጸት ጽፎታል። ያንን ሁሉ አመት ከህወሃት ጋር በእምነትና በትጋት ሲሰራ እንደነበር ቢነግረንም ከዚህ ውጭ የተናዘዘው ሃጥያት ግን የለም።
በምኒስትር ዴኤታ ማዕረግ ላይ ካለ ሰው የምንጠብቀው ከዚህ ላቅ ያለ ምስጢር ነበር። መጽሃፉ በሰብአዊ መብት ጥሰት ላይ ብዙ ትኩረት አልሰጠም። ሌላው ቢቀር የግል ፕሬሱ ይዘግባቸው የነበረው በካዛንችዙ ስውር መንግስት ስር የሚሰሙ ሰቆቃዎች፣ ስቃይና ግድያዎች ጸሃፊው እንደዋዛ አልፏቸዋል። እንደ እንጉዳይ ተክል በአንድ ሌሊት ብቅ ያለው የአባይ ጉዳይ ላይ ኤርምያስ አንድ ነገር ይላል የሚል ግምትም ነበረን። ይህንንም በዝምታ አልፎታል። ምናልባት የምስጢሩ ተቋዳሽ አይሆን ይሆናል። ምናልባትም በቀጣዩ ማስታወሻው ይመለስበት ይሆን ይሆናል። ስለ ሃይሌ ገብረስላሴ አድርባይነት በሚገልጸው ክፍል (ገጽ 285) ስለ አትሌቱ፤ “እንቁ እግር፣ አድርባይ ጭንቅላት” የሚል ርእስ በሚቀጥለው ማስታወሻ እመለስበታለሁ ብሎናል። ይህም ደራሲው ቀጣይ ስራ እንዳለው ያመላክተናል።
መጽሃፉ በርካታ የፊደል ግድፈቶች ይታዩበታል። አንዳንዶቹ ግድፈቶች የመልዕክቱን ትርጉሙ ሁሉ ቀይረውታል። ከዚያም አልፎ፤ በአማርኛ ተስተካካይ ፍቺ ያላቸው እንደ ዲሞቢላይዜሽን፣ ኔትወርክ፣ ኦረንቴሽን፣… የመሳሰሉ የባዕድ ቃላት በአማርኛ ተዛማጅ ትርጉም አልያም በቅንፍ ቢቀመጡ ይመረጥ ነበር።

ታዋቂው ፖለቲከኛና መምህር ወጣት አብርሃ ደስታ ዛሬ ፍ/ቤት ቀርቦ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀበት

0
0

Abrha Desta

በአራዳ መጀመሪያ ፍ/ቤት ችሎት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ይቀርባል ቢባልም ዘግይቶ 10 ሰዓት ከ25 ላይ ቀርቧል፡፡ ፖሊስ ሀምሌ 3 ቀን ፍ/ቤት ቀርቦ ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ በሽፋን ትሰራለህ በሚል በቁጥጥር ስር አድርጎ ለምርመራ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆበት የነበረ ሲሆን በ28 ቀን ውስጥም ምንም ማስረጃ ለችሎቱ አላቀረበም፡፡ በችሎቱ ላይ የአረና አመራር አቶ ካህሳይ፣የአብርሃ እህት በችሎቱ እንዲታደሙ ተፈቅዶላቸው ገብተዋል፡፡ አብርሃ ደስታ በእስርቤት የደረሰበትን ለችሎቱ ሲያስረዳ እያስገደዱ ቃል ተቀብለውኛል፣ ተደብድቤያለሁ፣ ከውጪ የመጡ የደህንነት ኃይሎች ምርመራ አድርገውብኛል፣ ጨለማ ቤት ለቀናቶች ነበርኩ፣ የማላውቀውንና ያላነበብኩትን እንደፈርም ተደርጌያለሁ፣ የጨጓራ በሽተኛ ሆኜ በግድ እንጀራ እንድበላ ተደርጌያለሁ በማለት ለፍ/ቤቱ አስረድቷል ፡፡ ፖሊስ እነዚህ ድርጊቶች በፖሊስ ጣቢያው እንደማይደረጉና ማስረጃ የሌላቸው ውንጀላዎች ናቸው በማለት ያስተባበለ ሲሆን፣ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ደንበኛቸውን የሚመረምረውን መርማሪ ስም እንዲገለጽ ቢጠይቁም የመርማሪውን ስም አንናገርም ይዞ ፍ/ቤት የሚያቀርበውን ፖሊስ ስም ብቻ ነው የምንናገረው በማለት መልሰዋል፡፡ አቃቤ ህግ ለምርመራ ተጨማሪ የ28 ቀን ቀጠሮ ጠይቆ ፍ/ቤቱ የ28 ቀን ቀጠሮውን ፈቅዶ ለነሐሴ 29 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት እንዲቀርብ አዟል፡፡ የፍርድ ቤቱን ሂደት ለመከታተል አረና፣ የአንድነት፣ የሰማያዊ፣ የመድረክ፣የጌዴኦ የፓርቲ አመራሮችና አባሎቻቸው፣ ጋዜጠኞችና ብሎገሮች በርካታ ሰዎች ተገኝተው አብርሃ ወደ ፍ/ቤት ግቢ በሚገባበትና በሚወጣበት ጊዜ በጭብጨባና አይዞህ በማለት አጋርነታቸውን ሲገልጹ ብርሃ ደስታም አንገቱን ዝቅ በማድረግ የታሰሩ እጆቹን ከፍ በማድረግ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ምንጭ፡-ፍኖተ ነጻነት

ላቂያ! (ሥርጉተ ሥላሴ)

0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 8.08.2014 (ሲዊዘርላንድ -ዙሪክ)

ይህቺ ተመስጥራ የኖረች እርዕስ በዬትኛውም መጸሐፌ ላይ የለችም። በዬትኛውም ወጋወጎቼም ላይ ታዳሚ ሆና አታውቅም። ቁጥብ ነበረች። ዛሬ ግን ከማህደረ የህሊና ሰሌዳ ብቅ ብላ እነሆ ለአደባባይ ትውል ዘንድ ቀይ ጃኖዋን ለብሳ ከመንበሯ ላይ ጉብ። ላቂያን የመረጥኩት የበለጠ ፍቅር – አትኩሮት – ትህትና – ተደማጭነት – እንክብካቤ ጥበቃ ሊሰጠው የሚገባ የተስፋ አምክንዮ ይዤ ስለቀርብኩ ነው። ይህቺን የምወዳትን ዬክት እርእስ ይዢ ብቅ ያልኩት።

1. መነሻ

10ዘመናዊቷን የደብረማርቆስ ከተማን ለማዬት የዳጎሰ ህልም ነበረኝ። አብዝቼ እሻቅልም ነበር። ስለምን? የሴቶች ዓለምዐቀፍ የርትህ አንደበት የተከፈተባት ታላቅ ባለውለታ የተግባር ማሳ በመሆኗ። የዴንማርኳ ርዕሰ መዲና ኮፐንሀገን የማህበረሰቡ ጸሐይ ለሆኑት አንስተ – ትጉኃን የአርነታችን ልዩ ጧፍ ነበረች። ዴንማርክ ሀገርነቷ በደሴት ውበት የተነጠፈላት ነው ማለት ልቻል ይሆን?

ዴንማርክ በተፈጥሮ የኃይል ማመንጫ ተጠቃሚነቷ የዘመናቱን ሱናሚያዊ ጥፋትን ለመታደግ በብዙ ሁኔታ መሰናዶዋን ያሟላች አብነታዊ ሀገር ስትሆን፤ በተገጣጣሚ ዬቤት ግንባታ ዘርፍም አንቱነቷ ቁንጮ ነው – ለአውሮፓውያኑ። በእንሰሳት ተዋፆ ምርትም የተባ ብቃት እንዳላት ይነገርላታል። ከዚህ በተረፈ የባሩድ መርዛማ ጪስ፤ የመትረዬስ አሲዳማ ሩምታ ፈጽሞ ያልደፈራት የሰላም ድንግል ምድር ናት። አምላክ መርቆ በፈጠራላት ጸጋዋ ንጹህ አዬርን የምትመገብ ደልዳላ ውብ ወ/ሮ ሀገር። ክረምት በሰማዩ ነጭ የአሻቦ አበባ – በጋ ደግሞ በተፈጥሮ ልምላሜ የፈካች። ታድላ!

የኮፐንሀገን ርዕሰ መዲናዋ ዴንማርክን ስታዩ ልክ ደብረ ማርቆስ እንዳላቸሁ ይሰማችኋል። ልዩነቱ እነሱ በ21ኛው ምዕተ ዓመት ላይ ያሉ ዘመኑ ለፈቀዳላቸውን ሥልጣኔ ተጠቃሚዎች ሲሆኑ ማርቆስዬ ደግሞ ገና ጎሳ ላይ ባለ በወያኔ ሃርነት ትግራይ ቡድናዊ አስተዳደር በቀል ከሚደቃቸው ከተሞች አንዷ መሆኗ ነው። ፍትህ – የራባት -የራቃትም።

በተረፈ የተፈጥሮ መልክዕ ምድራዊ አቀማመጧ፤ የከተማዋ አመሰራረትና ግራና ቀኛ ያሉት ዬቤቶች ሰልፍ ሁኔታ ክረምት ላይ ከዝናቡ ጋር ያለው የውቂ ደብልቂ ጠረን ሁሉ ቁርጥ ደብረማርቆስ – የዴንማርክ ርትዑዋ ከተማ ኮፐንሀገን። እናላችሁ የነፃነት ትግሉ ቤተሰቦች ገና ወደ ዴንማርክ ለመሄድ ስናሰብው ጀምሮ ነው በመንፈስ አብርን ቤተኛ የሆነው። ማንና – ማን? ይመጣበታል —-

2. ምልሰት

በ2009 ከታህሳስ 18 ቀን ጀምሮ አፈሩ መርግ ሆኖ ይክበዳቸውና የወያኔው ዞጋዊ ድርጅት መሥራች ሄሮድስ መለስ ዜናዊን ጨምሮ የኃያላን ሀገሮች መሪዎች በG20 ዓለምአቀፋዊ ጉባኤ ለመታዳም በዴንማርክ ርዕሰ መዲና ኮፐንሀገን ላይ እንደሚገኙ ከታወቀበት ቀን ጀምሮ የነፃነት ራህብተኛ ወገኖች በዬተዳራጁባቸው መድረኮች ሆነ ድርጅቶች ስንቃቸውን ማሰናዳት – ለጉዟችው የሚያስፈልገውን ትጥቅ ማሟላት ቀድመ ብለው ነበር ዬተያያዙት። በዬአውሮፓው ሀገር ነፃነት ከናፍቆቱ ጋር በህብረት መከረ። ዘመቻው ማዕከላዊ ከመሆኑም በላይ የተቃዋሚ ድርጅቶችንም ያሳተፈ ነበር። ዋና አዝማቻቸው እረኛው ጋዜጠኛ አህመድ ሲሆን ዬስምሪቱ ጠቅላይ አዛዥ ደግሞ የከረንት አፌርስ ዴስከሽን ፎረም ፊት ላይ ነበር። በዬአካባቢው ዝግጅቱ በግልና በወል ጦፈ። በቂ ፍላዬር ፖስተር በአይነት በብቃት ተዘጋጀ። ኮፐንሀገንን በፍትህ ፈላጊያኑ ኢትዮጵያዊ ድምጽ ቀውጢ ለማደረግ መንፈስ አሳምሮ ተሳለ። የኮፐንሀገን የነፃነት ትግሉ ልጆች ስምንት ብቻ ስለነበሩ ጎደሎውን ሁሉ ለመሙላት በትጋት በዬአካባቢው ይጎድለናል፤ አቅም ያስፈልገዋል ባልናቸው መሰረታዊ ጉዳዮች ሁሉ ከአገልግሏ ጀምሮ ሰፊ መሰናዶ ለዘመቻው ተደረገበት።

ቀኑ በጉጉት ሲጠበቅ ደረሰልን። አቶ መለስን ከሥፍራው ተገኝቶ እርቃናቸውን ማስቀረት፤ ቀልባቸውን መግፈፍ፤ በአለም አደባባይ ሊዘግቡ በተዘጋጁት ጋዜጠኞች አቤቱታውን ማስቀረጽ ጉልበታሙ ዓላማችን ነበር። በረዶው ታዲያ ጉድ ነበረ። በተለይ ለሲዊዝ ታዳሚ ኤክሲሞስ ምስጋን ይነሳው - 21 ግራድ።

አይዋ በረዶው በነፃነቱ ተጠቅሞ በተመቸው ሁኔታ ተደራጅቶ ማን ነክቶኝ ብሎ፣ ተራራ ሰርቶ፣ ምሽጉን አጠናክሮ ጠበቀን። ታዲያላችሁ ከበረዶው ተራራ የሚልከው በረዳማ ንፋስ ሰውነትን ፍሪዝ አደረገው። ተመሳስለን ቁጭ። ነጩን ባዘቶ ለብሰን በሰማይ አሻቧዊ አበባ ተሽሞንሙነን የጎጠኛውን መሪ ሴራ ለማራገፍ አቅማችን በእልህ አደራጅተን ማን ደፍሮን አለን – እኛው። ሰልፉ ዓለምዓቀፉ ጉባኤ እስኪያበቃ ድረስ በተከታታይ ቀናት የሚከውን ነበር። ውሏችን ከዛው ስለነበር የአርበኛን ስንቅ የተሸከመች ታሪከኛዋ አገልግሏም ተሰላፊ ነበረች። እኔው አጮልቄ ሳያት አገልግሏን እሷንም አይዋ የሰማይ አመልማሎ ጎሰም ያደርጋት ነበር። አልራራላት – ሲገርም።

እውነት ለመናገር የበረዶው ክምር የዴንማርክን ከተማ አስተዳደር በፍጹም ሁኔታ ያሸነፈ ጡንቸኛ ነበር ማለት ይቻላል። ሰፈር አድባሩ በተለይ መንገዱ በመልክ የለሽ ሁኔታ ተለነቆጠ። ታዲያንላችሁ አይዋ በረዶ ሌትና ቀን ከተሰለፍንበት እምንቀር መስሎት ሳይደክመው ያወርደዋል – ያወርደዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ሰውም መኪናም በማይደርስበት ቦታ በነጭ ተፈጥሯዊ አሻቧዊ አበባ ጋራ ምድሩ ተንቆጥቁጦ ለሽ ባሉት ወንዞቿ ላይ ሳይቀር  ነጭ አልጋ ተዘርግቶ በነጭ አልጋ ልብስ ተሽሞንሙኖ ስታዩት ናፍቆ- ገነት ከዚህ ደግሞ ምን ጣለህ ያሰኝ ነበር።

ጉዙው ደግሞ ሌላው ፈታኝ ጉድ ነበር። ብዙ መንገዶች ዝግ ነበሩ። በበረዶ ብቻም ሳይሆን ለጥበቃ ተብሎም። ስለሆነም የጋራ መጓጓዣዎቻችንም እንዲሁ ሞተራቸውን ለማስነሳት ሆነ ለማራመድ ጋዳ ነበር። እዛው በረዶ  ሳንዱቹ አለሁኝ ቢልም እጅ አልታዘዝለትም ብሎ አሻፈረኝ ስላለ ዬጉርሻዋ ዓይን ከእኛ ራህብ ይልቅ  ወደ አመልማሎው ያደላ ነበር። መሬት ነህና ወደ መሬት ትመለሳለህ አሰኘው። እንዲህ  ዬእናት ሀገር ልጆች በዬአሉበት – በዬተገኙበት ፈተናን ለማሸነፍ ስንዱዎች ናቸው። ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር እምለውም ለዚህ ነው።

ከሰላማዊ ሰልፉ ደግሞ ማታ ቅልጥ ያለ እመቤት ኢትዮጵያን ማዕከሉ ያደረገ የሰከነ ህዝበዊ ስበሰባ ይካሄዳል። መስተንግዶው ተሟልቶ። አዳር ላይ ሌላ ጨዋታ የለም። የቀጣዩ ቀን ሰላማዊ ሰልፍ በምን ሁኔታ ቢሆን የበለጠ ተደማጭነት ይኖረዋል ነበር። በዬት አቅጣጫ ቢሆን የዓለምን የሚዲያ አትኩሮት ቀልብ መሳብ ይቻላል ነበር የወልዮሹ ዕድምታ። ፈጽሞ ብዕሬ አቅም ኑሯት ልትገልጸው አትችልም የነበረው አመራር – አደረጃጀት – መተሳሰብ – መደማመጥ – ፍቅር – መከባበር – የወይይት ፍጭት እንዴት ነፍስን ይታደግ ነበር። ዕድለኛነቴን ዛሬ ላይ ሆኜ ሳስበው ዕጣዬ ሁሉንም ዓይነት ገጠመኝ እንዳጣጥም – እንድኖርበት አምላኬ የመፍቀዱን ሚስጥር ዕሴቱን ሳስተውለው ባልፍም ካለ ጸጸት እንዲሆን አድርጎልኛል። „አድርገህልኛልና አመሰግንሃለሁ“

እስካሁን ከታደምኩባቸው ብሄራዊ ሆነ ዓለምዓቀፋዊ የውጭ ሀገር ዜጎች ጉባኤዎች በሀገር ወስጥም ሆነ በውጭ ከገበሬው መንደር ቀጥሎ የዴንማርኩ የመንፈሴ ልዩ ሙሽራ – የጸደቀ ምዕራፍ ነበር ማለት እችላለሁ። ሌላ ዓለም ሌላ ውበት ነበረው። እናት ሀገር የሁለመና መሠረት ናትና! በስደት ሀገር ደግሞ የዚህ ጥልቅ የአብሮነት መንፈስ ሲገኝ የምድር ገነት ነው። ይህን መንፈስ እንዴት መልሰን ማምጣት እንደምንችል አምላክ ይርዳን። አሜን! ምክንያቱም በዚህ መስዋዕትንት ያላፈን መንፈስ ለማስቀጠል ያለው አሳር፤ የድልድይ ሰባራው ዘመቻ፤ የአቅም ብክነቱ … እሱ ባለቤቱ ይፍታው። የሚገርመው የዛ አቅም ሞገድ ጉልበታምነት በወያኔ አስተዳደር ተፈቅዶላቸው የስበሰባውን ሂደት እንዲዘግቡ የመጡትን ጋዜጠኞች እስከማሸፈት የደረሰ ነበር። መርምሩት —-

2. መዳረሻ

በዚህ ወቅት ከካናዳ ድረስ ፕሮግራሙን ከሰላማዊ ሰልፍ ጋር አደራጅቶ  ከእኛ ጋር ዴንማርክ የነበረ ምርጥ ኢትዮጵያዊ ወንድም ነበረን። እንደኛው ማደሪያ ዶርሚተሪ ተመድቦለት አብሮን ሰሜን አሜሪካን አውሮፓ ላይ ወክሎ በዕንባ ምጡ ታደመ። የዕንባ ምጥ ቀለበት የአህጉር ድንበር የለውምና። ድንቅ ልዩ ወንድም። የእኔ ጌታ ናፍቆቴን በፍቅር ጠልፌ አክብሮታዊ ምስጋናዬ ይደረስህ እላለሁ። ሌላው የአንድ ቤት ልጆች ስንገናኝ የነበረው የፍቅር ጥበብ፤ የጠረኑ ደም ግባት ዬጸዳሉ ኢትዮጵያዊ ጥሪኝ ለትውፊትነት ብቁ ነበር። ከረንት ልዩ እኮ ነው። መግቢያ ዓውደ ምህረት እኮ ነው። ለከረነት ዋጋ አነሰው። እስኪ ኢሳቶች ስለከረንት ህይወት ገባ ብላችሁ ቃለምልስ አድርጉ በተራቸው እነሱም ይጠዬቁ። ውብ አንባ ወርቅ መንደር ከረንት! ዬታሪካችን ዘለበት ነው ከረንት! የስደቱ የመከራ ዘመን በኽረ በልግ።

በ2009 ከታህሳስ 17 እስከ ፍጻሜው የዴንማርክ ውሎ በተቃውሞ ሰልፉና በህዝባዊ ስበሰባው ለመገኘት ከመላ አውሮፓ  የተውጣጡ ካናዳንም ጨምሮ የተግባር አርበኞች በግልም በድርጅትም ታደሙበት። „ኢትዮጵያዊነትን“ ማዕከላቸው ያደረጉ ደፋር ማህበራዊ ድህረ ገፆች፤ የኮሚኒቲ ራዲዮ ፕሮግራም አዘጋጆች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ተሳታፊ ነበሩ። ሞትም ቢሆን አብረን ብለው።

ዬኔዎቹ ዬነፃነት ራህብተኞች ወገኖቼ መነሻዬ ሆነ መድረሻዬ የወያኔ ልብጥ ሁለተኛ ቪዲዮ ነው። አሁን የወያኔ የጎጠኝነት ፍቅረኞች ዝርዝር አገኘን ብለው የሚያላዝኑት ስሰማ ወያኔ እዬተኛ ነው የሚኖረው ለማለት ልድፈረው። እንደነገርኳችሁ ገና ሃሳቡ ሲወጠን ቤተኛ ቤተሰብ ነበርን። ስንደርስ ደግሞ ለቅድመ መሰናዶ ምግብ ለማዘጋጀት ካሳለፍነው ሌሊት በስተቀር እዛው ዴንማርክ ዬሚኖሩትን ጨምሮ በአንድ ካንፕ ውስጥ ነበርን። ለእኔ ከሥጋ ዝመድና በላይ – በላይ  - በላይ ዓላማዬ ላቂዬ ነው።

ዶር. ሙሉአለምን ያገኘሁት በዚህ ወቅት ነበር። እንደሚታወቀው በዘመነ ቅንጅት ድጋፍ ድርጅቶች በዬአካባቢው ተደራጅተው ነበር። ከቅንጅት መራራ ስንብትም በፊትም ሆነ በኋላ አቅም በፈለገው ጅረት ተበትኗል። ኖርወይ ላይ ግን በዚህ ላቂያ በሆነ ብቁ ሙሴ አማካኝነት ሃይል አልባከነም። አቅም አልሾለከም፤ ዓላማዊ ድርጅታችን አልተናደም፤ ቤተሰባዊ ግንኙነቱ በማፍያ ሰላዮች አልተበከለም። ማህበራዊ ዘርፉ ተወሳክ አልበቀለበተም። የወያኔ ሴራም አላፈራበትም – እንዲያውም የወያኔ መርሃ ግብር በውጭ ሀገር ድቅቅ ብሎ አመድ ስንቁ የሆነበት መሰረታዊ አመክንዮ በዶር. ሙሉዓለም ነበር ማለት ልቻል። ኖርወይ ላይ የሚታዬው ቋሚና በተግባር የሰከነ የእኩልነት ዓውደ ምህርት የአብነቱ ተከታታይነት ስምረት ሚስጥር ይህ ነው። ዶር ሙሉዓለም አቅም ነው። እሱ እራሱ ስክነት ነው። ብቁ መሪም አባትም ነው። የቀለም ዕውቀት ተመክሮው አቅም እንዴት እንደሚፈጠር፣ ከዬት እንደሚገኝ፤ ከተገኘ በኋላም እንዴት መያዝ እንዳለበት፤ እንዴትም እንደ መክሊቱ ጥቅም ላይ መዋል እንዳለበት ለተግባር ሰልጥኖ የተፈጠረ ብቁ ሰው ነው።

ይህን ለምናውቅ – ለምንረዳ ሰዎች የሰሞናቱ ሚስጥር የግንቦት 7 ሰዎች በአውሮፓ ዝርዝራቸው ተገኜ  በማለት ወያኔ የሚረጨው ፍዝ መረጃ  ጭድ ነው። የወያኔ ዘገባ ቀለሙ ያለቀ ቀፎ ነው።

እኛ የነፃነት ትግሉ ቤተሰቦች ምን በመዳፋችን እንዳለን ጠንቅቀን እናውቃለን። ዛሬ አይደለም ይህ የነፃነት ትግሉ የተግባር ላቂያ ወንድማችን የምናውቀው ….. እኔ እራሴ በ2010 በጸጋዬ ድህረ ገጽና ራዲዮ ፕሮግራም ቃለ ምልልስ አድርጌለት ነበር። ዶር. ሙሉዐለም የምርምር ሰው ስለመሆኑ በቃለ ምልልሱ ተካቷል። የጸጋዬ ድህረ ገጽ ሆነ ራዲዮ ፕሮግራሜ ታዳሚዎች የምርምር ሰው – ሳይንቲስት ስለመሆኑ በሚገባ ያውቃሉ። ዛሬ አይደለም ወያኔ ለእኛ የሚነገረን አሳምረን ጌጣችን – ክብራችን – ኩራታችን – ተስፋችን እናውቀዋለን። እንዲህ ላለ ብርቅ ወንድም ምንም እንኳን በቅርቡ ሁነን ልንረዳው ልናግዘው ባንችልም በመንፈሳችን ሰሌዳ በውስጡ ስላለ ሰንደቃችን አድርገን እንደታቦት የምንከበክበው የተከደነ ሃብታችን ሲሳያችን ነው። ጥበቃው ደግሞ የመዳህኒተአለም ነው።

ክብርት ዳኛ ብርቱካን ሜዴቅሳ ታስራ በነበረችበት ጊዜ ቤተሰቧ ምንም ዓይነት የኢኮኖሚ መስተጓጎል ሳይደርስበት ልጇ ሃልዬ የተገባውን ሳታጣ እንድትማር ያደረገው በቋሚ የተግባር ጌታው በዶር. ሙሉአለምም የሰከነ የአመራር ክህሎተ -ብቃት ነበር። እንዲያውም የመጀመሪያ ልጁ ባለው ለሴቶች ቅናዊ አክብሮታዊ ታማንነትም ምክንያት ማን ብሎ እንደጠራት እናውቃለን። አብሶ ለሴት ታጋይ እህቶቹ ሲመሰክር አንደበቱን ከፍቶ፤ ሲከታተል መንፈሱን ውስጡን በፍቅር በልግስና ሰጥቶ በልዩ አክብሮት ነው። በዚህ ዘርፍም ክህሎታዊ አንባሳደራችን ነው ብዬ ደፍሬ መናገር እችላለሁ።

ያ ብርቅና ድንቅ ሳይንቲሰት ከእኔ ከትቢያዋ ከማህይማ ጋር ነበር አብሮ በዛ ብርዱ በሚጋርፍበት ቦታ የታደመው። እራሱን ዝቅ አድርጎ ለኢትዮጵያ ዬዕንባ ዬምጥ ብሄራዊ ጥሪ በግንባር ቀደምትንት መሰለፉ ኢትዮጵያ ሀገራችን ፈጣሪያዋ የማይረሳት መሆኑን የሚያሳይ የሃቅ ዬወርቅ እንክብል ነው። ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ልጆቹን እንዴት ይጠብቅ – እንዴትስ ኃላፊነቱን ወስዶ ይንከባባከብ እንደነበር ላሰተዋለው ዶር. ሙሉ ዓለም የሥጦታ ሥነ – ጥበብ ነው ማለት እችላለሁ። እኔ በኖርዎይ ልጆች አዘውትሬ እቀናለሁ። እዛ ብሆን እልምአለሁ።

ወገኖቼ የእኔዎቹ ያ ሰላማዊ ሰልፍ የለዬለት ነበር። ገንዘባቸውን ከስክሰው ብቻ ሳይሆን ዴንማርኮች 8 ብቻ ስለነበሩ ሌሎችንም ሃላፊነቶች ወስደው የቆረጡ – የወሰኑ የኢትዮጵያ ልጆች ለጦርነት ነበር የሄዱት። ስለዚህ ይህ ዕንቁ ሳይንቲስት ዬኢትዮጵያ ብርቅዬ ልጅ ዬእናቱን የምጥ ዘመን የጸነሰ፤ ችግሯን ለመጋራት የቆረጠ፤ ማናቸውን መስዋዕትንት ለመቀበል የወሰነ የሰብዕዊነት ተሟጋች ተምሳሌት፤ የሙህርነት ህይወታዊነት ናሙና ልዩ ምልክታችን ስለመሆኑ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያውቀው አበክሬ በአጽህኖት ልገልጽ እሻለሁ። በዛ ሰላማዊ ስለፍ እኮ ከሳይንቲስቱ ጋር ብዙ ሚዲያዎች ቃለ -ምልልስ እድርገዋል። ዬት ሄዶ ነበር ወያኔ? ለነገሩ 5ኛ ክፍል ላይ እንዴት ተብሎ …..

ሌላው ሁለተኛው ላቂዬ ደግሞ እኔ እንኳን ቅዱስ ሚኬኤል ነው የምለው ግሩምዬ ነው። ዛሬ አይደለም የጉርምዬን  ዬአይቲ (IT) ባለሙያነት ሽፍታው ወያኔ የሚነግረን። እኔ እንዲያውም እንዳገኘሁት ነበር „አንዲት የነፃነት ታጋይ ሴት ድህረ ገጽ ኖሯት ድህረ ገፆን ሊንክ አልደረጋችሁም። ደግሞ የልጆች ፕሮግራምም አላት እሱን እንኳን እንዴት?“ ብዬ ነበር ዬወቀስኩት። በዕድሜ ታናሼ ነው ገሩሜ። በተግባሩ ደግሞ ከድርጊት የበቀለ ታላቄ። ይህን ጥያቄ እንዳገኘሁት ያነሳሁለት ሙያውን አሳምሬ ስለማወቀው ነበር። ወያኔ የግል ልብሱን አደፈ ብሎ ቆሻሻ ውስጥ ጨምሮ በሌላ ቀን ከቆሻሻ ቅርጫት ውስጥ አውጥቶ መልሶ ይለብሰዋል ልበልን?

ከዬት ይመጣል ጫካና ሀገር መምራት አራባና ቆቦ ነው ….

ወያኔ የሚያንደፈድፈው፣ ዛሩ እንዲህ የሚቀሰቀሰበት ሙያተኞችን ትጥቅ አስፈትቶ ለእሱ ለራፊ ለፍርፋሪ እንዲያጎነብሱ ማድረግ አለመቻሉ ነው። ሙሁሮቻችን እውቀታቸውን ሃገራቸው መሬት ላይ ተግባራዊ ማደረግ ባይችሉም ቁጭታቸውን ሆነ እልሃቸውን መወጣት የሚችሉት በነፃነት ትግሉ ዬሙያቸውን ሃላፊነት በተባ ድርጊት ማዋህድ ሲችሉ ብቻ ነው። ይህ ደግሞ ለወያኔ አብሾው ነው ያንደፈድፋዋል።  …. ግሩሜ ግን አድርጎታል – አሳብዷቸዋል። ስለዚህ ይህ ቀንበጥ ወጣት ታሪኩም ትውልዱም ዕንባ ያማጠውን ጥሪ የተገበረ የድርጊት ቀንድ እንዲሆን አድርጎታል። ስታዩት እራሱ ወርቅ ነው። ፍልቀቱ ነገን ያበራል። የእውነት የተግባር ጸዳሉ ሌትና ቀን የሚያበራ የሚንቦገቦግ የሰብል አዝመራ ነው። ግሩሜ አዝመራ ነው። እሱም ታዳሚ ነበር በኮፐንሃገኑ የዴንማርክ የተቃውሞ ስለፍም ብሄራዊ ስበሰባችንም ላይ ነበር። እኔ በአካል የማውቀውም እዛ ነው ከተባረከው የዴንማርክ የተቃውሞ የዕንባ ምጥ ጥሪ ላይ።

ግሩሜ ማለት ሲደመር – ሲደመር፤ ሲባዛ – ሲባዛ ሥራ ነው። ሃብትነቱ ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው። የግሩሜ የትኩሮት አቅጣጫ አንደኛው ሰብዕዊነት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ልዐላዊነት ነው። የደንበር ጉዳይ ለግሩሜ ደሙ ነው። በቃ! እኔ እራሴ ስለ ሰባዕዊነት መረጃ ስፈልግ እማገኘው ከእሱ የመረጃ ቋት ነው። አሁን ለዛ ራሱን በቤንዚን በማቃጠል ሰምዕትነቱን ስለገለጸው ስለ ዬኔሰው ገብሬ ማን ቋሚ ሁነኛ አለው? ለግሩሜ የኔሰው ገብሬ የጭንቅላቱ ህሊና ነው እንዲህ ልግለጸው። ግሩሜ ረቂቅ የብሩህ ተስፋ ብርሃናማ ማዕረግ ነው።  እና ጭዶቹ ሳታውቁት ቀርታችሁ ነው ድህረገጹን boycott እንዳይታይ ያደረጋችሁት – ታላግጣላችሁ …. ተረት ተረቶች fantasise/ize ስልችት ብሎናል ይህን ቆርጦ ቀጥል የጭቃ ለጭቃ ጨቀጨቅ ጉዟችሁ —-

3. ክወና

ሁለቱም ወንድሞቼ ለሥም – ለዝና – ለታይታ – ለዕውቅና አይደለም የሚደክሙት። ኑሯቸውን የሰጡት ዛሬ በወመኔው ወያኔ ለሚጠቀጠቀው „ኢትዮጵያዊነት“ ነው። እነሱ የአደራ የተግባር ሙዳዮች ናቸው፤ የበቀል ብቅሉ ወያኔ በንቀት የእግር ገንባሌ ያደረገውን ሰንደቅአላማችን፤ በተጨማሪም ጨርቅ ተብሎ በሄሮድስ መለስ ስላቅ የተንቋሸሸውን ብሄራዊ ዓርማ እነዚህ ተስፋዎች ወደ ክብሩ ለመመለስ ነው ውስጣቸውን ለነፃነት ትግሉ የሸለሙት። በማናቸውም የርሃብ መስክ ሁሉ እንደ ጥንቸል ሰንሰለታማ የመከራ ሙከራ ለሚደርግበት ሀገራችን ኢትዮጵያ ብሩህ የነገ ቀን ነው የሚባትሉት። በወያኔ ለተገፋችው ለተፈናቀለችው እናት ምድር ነው የሚባትሉት። ክብሯ ለተገፈፈው መሬት ነው ከፊት ለፊት ወጥተው የሚታገሉት። ውለታቸው ጥልቅ ፊኖሚናል ነው።

ስለዚህ ያ — እሮ አሮ የተመለሰበትን ካሳ ለማግኘት ቆራርጦ በሚያቀርበው ልብድ ዘገባ መረታት መፈታት ለአፈታም አይገባም። ነገ እነዚህ የቁርጥ ቀን ልጆች በባዶ ሳጥን ላይ ባለው የሙት መንፈስ  እዬገላበ ያለው የትግሬ ነፃ አውጪ ድርጅት ወያኔ ሞት ሆነ ዬእድሜ ልክ እስራት ሊፈርድባቸው ይችላል። ጉዞው ወደዛ ነው። ሲያሰኘውም የሰው ዘረፋውን ወይንም ዬማጥቃት መርዙን አጋጣሚ ጠብቆ ይፈጽማል – በብዙ መልኩ። ትውልድን መንቀል ነው ተልዕኮው።

ግን ግን የኔዎቹ – ክብረቶቼ አንድ ነገር ወያኔ በቀል ተብሎ ሥሙ ቢቀዬር ምን ይመስላችኋል? ወያኔ እኮ የበቀል ብቅል እኮ ነው። ስለሆነም የበቀሉ መረጃ፤ የበቀሉ የፍርድ ሂደት ሰለባ ላለመሆን የበቀሉ ዘገባ አራጋቢና አሽቃባጭ ላለመሆን  ደጉ ጨዋውና ቻዩ የኢትዮጵያ ህዝብ መሰናዳት አለበህ እላለሁ።

አንተን እዬገደለ ነው የበቀል ብቅሉ ወያኔ ለአንተ ቆሜአለሁ የሚለው -። አንተን እዬደረመሰ ነው ከእኔ ወዲያ ነፃነት ሰጪ ላሳር እያላ የሚደለልህ – የበቀል ብቅሉ ወያኔ። ስለዚህ በጥብጦ ሊግትህ የሚሻውን መርዝ በቃህኝ! ብልህ ልታስቆመው የምትችልበት መንሹም ያለህ ከእጅህ ነው።

በተረፈ በኮፐንሀገኑ የተቃውሞ የዕንባ ዬምጥ ጥሪ ላይ የተገኛችሁ ስበሰባውንም ሆነ የተቃውሞ ስልፉንም እንዲሳካ ያደረጋችሁ ብዙኃኑ የነፃነት አርበኞች፤ የንብ አውራ የነበረውን ጋዜጠኛ አህመድንም አክዬ እንዲሁም የኮፐን ሀገን የነጻነት ትግሉ ብርቅዬ ልጆች አዘጋጆች በተጨማሪም ድርቡን ሃላፊነት የወሰዱት የሲዊዲን ናፍቆቶቼን በድጋሚ አመሰገንኩ። ናፍቅኩኝም።  …. ታሪካችን ይፍልቃል …. አይዞን! የበቀል ብቅሉ ወያኔ እኛን አለማሸነፉን የሚረጋገጠው ማናቸውንም የድውይ ወያኔን መረጃ ማፍሰስ – ማባከን – ማክሰል ስንችል ብቻ ይሆናል። ትጋት ስንቃችን፤ ጥንካሬ ቀለባችን ጽናት ትጥቃችን  ይሁን። በዬትኛውም ቦታ በዬትኛውም ሁኔታ ዬአርበኞቻችን ተስፋ የመጠበቅ ግዴታ ይኖርብናል!  www.tsegaye.ethio.info Aktuell Sendung www.lora.ch.tsegaye

የነፃነት ባለውለታው ሰንድቅዓላማችን እንዲህ ያምርበታል! http://www.zehabesha.com/amharic/archives/33255

 

ውዶቼ የኔዎቹ  - እጣታችሁን እባካችሁ  ከተግባር ጋር አቆራኙት። ፍጥነት …. እሺ – እንበርታ!

http://ecadforum.com/2014/07/31/urgent-campaign-to-call-fax-white-house/

 

ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር ኢትዮጵያዊነት!

ጀግኖቻችን ቋሚ ዬህሊናችን መንገዶች ናቸው!

ነፃነት ያለው ማንነት ለነፃነት ክብር አለው። ግን የነፃነት የቃና መንፈስ ከተገለጠለት ብቻ!

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

የአማራ ክልል አመራሮች ከግንቦት7 የኦህዴድ ደግሞ ከኦነግ ጋር እያበሩ ነው ሲል አቶ አዲሱ ለገሰ ያዘጋጁትና ለጠ/ሚ አማካሪዎች የተላከው ሰነድ አመለከተ

0
0

ነሃሴ ፩(አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰነዱ ላይ ኢህአዴግ የአመራር ችግር እንዳጋጠመው፣ የትራንስፎርሜሽኑ እቅድ አለመሳካቱ

እንዲሁም በጋምቤላ

ተማኝ መሪ መጥፋቱ ተዝርዝሯል።

ethsatበሃምሌ ወር መጨረሻ የተዘጋጀው ሰነድ ግልባጭ ለጠ/ሚኒስትሩ አማካሪዎች ለአቶ በረከት ስምኦን፣ ለአቶ ደስታውና ለአቶ ኩማ ደመቅሳ ተደርጓል።

የቀድሞው ም/ል ጠቅላይ ሚኒስትርና የኢህአዴግ የፖሊሲ ስልጠና ክፍል ሃላፊ የሆኑት አቶ አዲሱ ለገሰ ” የኢህአዴግን ተቃዋሚ ሃይላት ማንኮላሻ አቅም ግንባታ እና የአመራር

ግንባታና የትራንስፎርሜሽን ጉዞ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ የፖሊሲ አማካሪዎች የቀረበ የሚለው ባለ 39 ገጽ ጽሁፍ፣ ኢህአዴግ ከላይ እስከታች የአመራር ችግር እንደገጠመው

በዝርዝር ያቀርባል።

ጽሁፉ በመግቢያው “አገራችንን በፈጣን ቀጣይነት ያለውና ህዝቡ በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበት የእድገት ጉዞ ከድህነት አላቆ በተራዘመ ሂደት ከበለጸጉት አገሮች ጎራ ለማሰለፍ ይህንን ለማድረግ

የሚያስችል አላማ፣ ስትራቴጂ ስልቶችና ፖሊሲዎችን መቀየስ ይጠይቃል። በሌላ አነጋገር አቅጣጫውን በትክክል የሚያመላክት መስመር መቀየስ የትራንሰፎርሜሽን ስኬት የመጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ነው።

መስመሩን ለመቀየስ ይህንኑ ማድረግ የሚችል ብቃት ያለው አመራር ይጠይቃል። ኢህአዴግ በዚህ ፈተና ውስጥ ነው።” ብሎአል።

ሰነዱ ” ለአብነትም እነ አቶ መላኩ ፈንታን ማንሳት ይበቃል” ይልና ” ይህን ተከትሎ በአገሪቱ ያሉ አመራሮች ለመቀበል አለመቻላቸው እና የኡመድ ኡቦንግ ሃገር መክዳት፣ በጋምቤላ

ክልል ያለው አመራር

ታማኝና አስተማማኝ አለመሆኑ፣ የአማራ ክልል አመራሮች ከግንቦት ሰባት ጋር የተያያዘ አመራር መገኘት፣ የኦህዴድ አመራር ከኦነግ ጋር በማበር እና በአማራ ላይ የደረሰውን በደል በቸልታ

መመልከት” በማለት

ይጠቅስና “በአሁኑ ሰአት በትግራይ ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ( የአመራሩ ቸልተኝነት እንደተጠበቀ ሆኖ)፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በሃረሬ ምርጫውን ማሸነፍ የሚችል አመራር ድምጽ የማግኘት

እድል አለው” ብአሎል።

ሰነዱ “የትራንስፎርሜሽን ትግል በውል ይጀመራል እንጅ አይጠናቀቅም ቢባልም በስጋት በተቀመጡት ክልሎች አሁንም አፋጣኝ ስራ ካልተሰራ ኪሳራ ሊያመጡ ይችላሉ” ብሎአል። የአመራሩ

ደካማነት የትራንስፎርሜሽን

ጉዞ ሳይሳካ እንዲቀር አድርጎታል የሚለው ሰነዱ፣ ድርጅቱ ሰዎችን የሚመለምልበትና የሚያሰለጥንበት መንገድም ብዙ ችግሮች ያሉበት በመሆኑ፣ የምልመላ ዘዴውንና የስልጠና መንገዱን

እንዲቀይር ይመክራል።

ኢህአዴግን በመሰረቱ አራቱ ድርጅቶች መካከል ያለው ትውውቅ ደካማ በመሆኑ ከከፍተኛ እስከ መካከለኛ አመራር ያሉት በአንድ ማእከል ስልጠና እንዲሰጣቸው እየተደረገ መሆኑንም

ተጠቅሷል። ኢህአዴግ እጅግ በጣም

የሚበዛው አባሉ አርሶ አደር በመሆኑ ፣ የፖለቲካ መሪዎችን በብዛት ለመፍጠር አለመቻሉን የሚጠቅሰው ሰነዱ፣ ከእንግዲህ በዩኒቨርስቲዎችና በከተሞች ላይ ትኩረት ተደርጎ ሰዎችን

የመፈለጉ ስራ እንዲጀመር ያሳስባል።

Source: Ethsat


አቶ ሬድዋን ሁሴን በቨርጂኒያ ውርደት ገጠመው፤ ኢትዮጵያውያኑ ልክ ልኩን ነገሩት (ቪዲዮ)

0
0

ስንታየሁ ከሚኒሶታ

አቶ ሬድዋን ሁሴን ለሆዱ ያደረ በአራዳ ቋንቋ ‘ችስታ የወያኔ ተላላኪ’ መሆኑን ያሳየው ዛሬ ነው። በአርሊንግተን ቨርጂኒያ። አሜሪካን ውስጥ “ችስታ” ወይም ገንዘብ መቋጠር ከፈለክ የተራረፉ ልብሶችን የምትገዛበት ሱቅ ማርሻልስ ነው። የኬቨን ኪለር፣ ባናና፣ ቦስ፣ ናይኪ፣ አዲዳስ፣ ቶሚ፣ ኤክስፕረስ እና ወዘተ ታዋቂ የልብስና ጫማ አምራች ድርጅቶች በመደብሮቻቸው በሰዎች ልክ (ሳይዝ) የሰሯቸው እቃዎች ወደ ማለቂያ (ፋሽናቸው ሲያልፍ) የሚልኩት ወደ ማርሻልስ ስቶር ነው። ባጭሩ ማርሻልስን በሃገርኛ “ምናለሽ ተራ” ልትሉት ትችላላችሁ።

አዜብ መስፍን አሜሪካ ስትመጣ ጆርጅ ታውን ወርዳ በጣም ውድ የሆኑ ሱቆች ገብታ በ$10 ሺህዎች የሚቆጠሩ ዶላሮችን ታፈሳለች – የሰረቀችው ስላላት። ቴዎድሮስ አድሃኖም ከደሃው ሕዝብ ከሰረቀው ገንዘብ ቀነስ አድርጎ ኒውዮርክ ላይ ጄ ፕሬስ ቡቲክ ገብቶ በሺዎች ዶላሮች ለልብሶቹ አፍሶ ይወጣል። ታይም ስኩዌር ሄዶ ፎቶ ይነሳል። ተላላኪው ሬድዋን ሁሴን ግን ‘ቺፕ’ ብለው አሜሪካውያን በሚጠሩት ማርሻል የተራረፈ ልብስ ገዝቶ ይወጣል:: ዛሬ የሆነውም ያ ነው። ሰውዬው አሜሪካ መጥቶ አዲስ አበባ ላሉት ባለስልጣኖች ከአሜሪካ የገዛሁት ልብስ ብሎ ለማሳየት ከአሜሪካው ምናለሽ ተራ ሱቅ ልብስ ሊገዛ ገብቶ ተዋርዶ ተመለሰ። ኢትዮጵያውያኑ ተጋፈጡት። ሌባ መሆኑን፤ ገዳይና የገዳይ አገልጋይ መሆኑንም የፊቱ ቆዳ የሳሞራ የኑስን ልብስ እስኪመስል ድረስ ነገሩት።

እንደለመደ አፉን አይከፍት ነገር ያለው አሜሪካ ሆነበት፤ እንዳይደነፋ ኢቲቪና መቀሱ የሉም። ውርደቱን ከኤክስፕረስ በታላቅ ቅናሽ የገዛውን ሰማያዊ ልብስ እንደለበሰ ተከናንቦ ተመለሰ። ወይ ሬድዋን፤ አዜብ ጆርጅ ታውን፣ ቴዎድሮስ ጄፕሬስ ሲገበያዩ አንተ ቺስታና ሆድ አደር ስለሆንክ በማርሻል ውርደትህን አከናነቡህ አይደል? ገና ምን አይተህ? ኢትዮጵያውያኑ የሳሞራ የኑስን ልብስ እንዲመስል ያደረጉልህ ቆዳህ ገና ወደ የት እንደሚሄድ አብረን እናየዋለን።

ሬድዋንን የተጋፈጡትን ብርቱ ኢትዮጵያውያንን እያደነቁ፤ የወያኔ ተላላኪዎችን የማወረዱ ሥራ እንዲቀጥል አደራ እላለሁ። ቪድዮውን እነሆ።

redwon Hussein

እንግሊዝ እና ጫት፡ ጫትም “አሸባሪው”ተክል ይባል ይሆን?

0
0

ከረ/ፕሮፌሰር መኩሪያ መካሻ አ.አ.ዩ

በኢትዮጵያ፣ በኬንያ፣ በሱማልያ፣ በጅቡቲና የመን የሚዘወተረው አነቃቂው ጫት ምሥራቅ አፍሪካን አልፎ አውሮፓን ሲያስጨንቃት ኖሯል፡፡ ዛሬ ግን የጫት አድባር በአውሮፓ አልቆመለትም፡፡ ከአውሮፓሀገሮች እስከ ዛሬ ድረስ ጫትን በህገ-ወጥነት ሳትፈርጅ የቆየችው እንግሊዝ ሰሞኑን የመጨረሻውን ውሳኔ አስተላልፋለች፡፡ ጫትን የቃመም ሆነ የነገደ የሚቀጣና ይህ አደገኛ ዕጽ የተከለከለ መሆኑን ይፋ አድርጋለች፡፡
Khat
የጫት ተጠቃሚዎች ጫትን እንደሚያሞካሹት ‹‹ጫትን ስንቅም ንቁ፣ ደስተኛና ተናጋሪ ያደርጋናል›› ቢሉም ከእንግዲህ በኋላ በሀገረ እንግሊዝ ጫትን መቃምም ሆነ ማዘዋወር የተከለከለ ሁኗል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በተለይ ለእንግሊዝ ገበያ በቀጥታ ከኬንያ የሚያቀርቡ የጫት ገበሬዎች በውሳኔው ተደናግጠዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ናሲር አደም የተባለው የካርዲፍ የሶማሌ ማህበረሰብ መሪ አብዛኛዎቹ የሶማልያ ማህበረሰብ አባላት ጫት በመታገዱ ደስተኞች ናቸው፡፡ ጫትን በብዛት መቃም በሰዎች የአእምሮ ህመምና የቤተሰብ መፍረስን ያስከትል እንደነበር ጨምሮ አስረድቷል፡፡
ናሲር እንዳለው በቀድሞ ጊዜ አዛውንቶች ነበሩ የሚቅሙት፣ በአሁኑ ዘመን ግን ወጣቶች ተለቀውበታል፡፡ የእንግሊዝ የሶማሌ ማህበረሰብ ጫት እንደታገድ ሲታገል ቆይቷል፤ ፖሊስ፣ የጤናና የፓርላማ ባለስልጣናት ሕብረተሰቡን በማዘጋጀት በኩል ምን አድርገዋል? ሲልም ጠይቋል፡፡
በተፃራሪው የጫት ኤክስፖርት ነጋዴው ማቲዎስ ጊቶንጋ ‹‹ጫትን ማገድ ሰብአዊነት አይደለም፡፡ የእንግሊዝ መንግሥት ዕገዳውን ቢያንስ እንኳ እኛ እስከምንዘጋጅ ድረስ ለአንድ ዓመት ሊያነሳ ይገባል›› ሲል አምርሮ ተናግሯል፡፡ ሌላኛው ሴት ቤሲያ ካቱሬ ደግሞ ‹‹ተስፋዬን አጥቻለሁ፡፡ ልጆቼን እንዴት እንደምመግብና የትምህርት ቤት ክፍያ እንደምከፍል አላውቅም›› ብላለች እገዳውን ተከትሎ፡፡

የእንግሊዝ የዕጾች ጉዳይ ክትትል ኃላፊ ቺፍ ኮንስታብል አንዲ ቢሊስ ደግሞ ፖሊስ ከጤና ሙያተኞችና ከማህበረሰቡ አባላት ጋር ስለ ዕገዳው ተቀናጅቶ እየሠራ ነው ሲል አስታውቋል፡፡ በነገራችን ላይ በብርስቶል ከተማ ከዚህ ቀደም ጫት የሚሸጡ 30 የንግድ ተቋማት በዕገዳው ምክንያት ሥራቸውን እንደሚያቆሙ ገልፀዋል፡፡

በሀገረ- እንግሊዝ ጫት መታገዱን በተመለከተ የተለያዩ አስተያየቶች ያሰነዘራሉ፡፡ አንዳንዶቹ ጫት አንደ አደገኛ ዕፅ ተወስዶ መታገዱ ትክክል አይደለም ሲሉም ተደምጠዋል፡፡ ለምሳሌ ያህል ዳኒ ኩሽሊክ የተባለ የፀረ- ዕፅ ዝውውር ፋውንዴሽን ኃላፊ ሲናገር ‹‹አልኮል መጠጥ በሰፊው ጥቅም ላይ እየዋለ ጫት መታገዱ ትክክል አይደለም!›› ብሏል፡፡ አይይዞም የተወሰኑ ህዳጣን የሕብረተሰብ ክፍሎችን ማለትም ሶማሌውያንና የመናውያንን ጫት ጋር በተያያዘ መወንጀል አይገባም ሲል ተችቷል፡፡

በወጣው የዕገዳ ህግ ጫትን ለመቃም ይዞ የተገኘ 60 ፓውንድ ይቀጣል፡፡ የእንግሊዝ የሀገር ውስጥ ሚንስትር ቴሬዛ ሜይ እንዳሉት ጫት በእንግሊዝ ብቻ ሳይሆን በኔዘርላንድስ፣ በአብዛኛዎቹ የአውሮፓ ሕብረት ሀገራት፣ በቡድን 8 ሀገራት ማለትም ካናዳና አሜሪካን ጨምሮ ጫትን አግደዋል፡፡ በአዲሱ ህግ መሰረት በእንግሊዝ ሀገር ጫትን ማዘዋወር ለ14 ዓመት እስራት እንደሚዳርግ ታውቋል፡፡

በሀገራችንም ሆነ በአካባቢው ሀገሮች በስፋት የሚመረተውና ኤክስፖርት የሚደረገውን ጫት ማገድ ለምን አስፈለገ? ብሎ መጠየቅ ተገቢነት አለው፡፡

በብዙዎች ዘንድ ካት፣ በሀገራችን ደግሞ ጫት፣ በኬንያ ሚራ የሚባለው ተክል እጅግ ስለ ተከሉ ሲንቆላጰስ ደግሞ ‹‹የአረቦች ሻይ›› በመባል ይታወቃል፡፡ ጫት በበለፀጉት ሀገራት ቢታገድም በሀገራችንና በአካባቢው መመረቱና ጥቅም ላይ መዋሉ ቀጥሏል፡፡ በአብዛኛዎቹ ተጠቃሚዎች ዘንድ ከጫት ይልቅ አልኮል ጉዳት አለው ይባልለታል፡፡ ጫት እንደ ቡናና ሻይ ሁሉ ጉዳት የለውም የሚሉ ሞልተዋል፡፡

በእንግሊዝ የዕጽን አላግባብ መጠቀም አማካሪ ምክር ቤት ግምት ወደ ሀገረ- እንግሊዝ በዓመት 2,560 ቶን ጫት ይገባል፡፡ ከዚህ ውስጥ የእንግሊዝ መንግስት 2.5 ሚልዮን ፓውንድ ቀረጥ ያገኝበታል፡፡ ብዙ በእንግሊዝ የሚኖሩ ሱማልያውያን፣ ኢትዮጵያውያንና የመኖች በጫት ንግድ የሚተዳደሩ በመሆኑ እነዚህን ነጋዴዎች ስራ ፈት ያደረጋቸዋል፡፡ ከሁሉም በላይ ዕገዳው በምሥራቅ አፍሪካ በጫት ምርት የተሠማሩ 500,000 የሚደርሱ ገበሬዎችን ይጎዳቸዋል፡፡

ጫት አእምሮን ይረብሻል፣ ያሰንፋል፣ ድብርት ያሳድራል፡፡ በተጨማሪም አፍን ማሽተት አልፎ ጥርስን ይጎዳል፡፡ ብዙዎቹ ቃሚዎች ጥርሳቸው የሻገተና የወላለቀ ከመሆኑም በላይ የአፍ ካንሰር ያመጣል ተብሎ በተመራማሪዎች ተነግሯል፡፡ ጫት ከአእምሮ ወታወክ (psychosis) በሽታ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው በሚል የተረጋገጠ ማስረጃ ግን አልቀረበም፡፡ በአንድ በየመን ሀገር በተደረገ ጥናትና ለዓለም ጤና ድርጅት የቀረበው ማስረጃ እንደሚያመለክተው 90 በመቶ የሚሆኑ ጎልማሳ ወንዶች ለሦስትና አራት ሰዓታት ጫት ይቅማሉ፡፡ ዶክተር ጓንኤይድ ከሰንዓ ዩኒቨርስቲ ሲናገሩ ‹‹ጫት ቃሚዎች መጀመሪያ ደስታ፣ ከዚያም በድብርት ስለሚያዙ ለአእምሮ መታወክ ተጠቂዎች ሊሆኑ ይችላሉ ብለዋል፡፡ በእንግሊዝ ሀገር የተደረገው ጥናት የሚያመለክተው ብዙ ወጣቶች ከትምህርት እንዲቀሩና ቤተሰቦቻቸው ደግሞ ሥራ ከመሥራት ይልቅ በጫት ደንዝዘው ቤት እንዲውሉ ማድረጉን በተጨባጭ ማስረጃ ያቀርባል፡፡ በተጨማሪም አል-ሻባብ የተሰኘው አሸባሪ ድርጅት በጫት ኤክስፖርት ገቢውን እንደሚያጠናክርም ይጠረጠራል፡፡ አል-ሽባብ ለሽብር ድርጊቱ ማጠናከሪያ ጫትን የሚጠቀም መሆኑ ከተረጋገጠ ጫት- አሸባሪው ዕጽ መባሉ አይቀሬ ይሆናል፡፡

Health: ትዳር ለመመስረት ፍቅር ምን ያህል አስፈላጊ ነው?

0
0

Decisions of Love to make our Marriage Life Successful
ከሊሊ ሞገስ

ስኬታማ ትዳር ከአንድ ሰው ጋር ደግሞ ደጋግሞ በፍቅር መውደቅን ይጠይቃል:: በልጅነታችን ሁላችንም ፍቅር ካለ ሁሉ ነገር አልጋ በአልጋ ይሆናል የሚል ህልም ነበረን፤ እውነታው ግን ትዳር ቀላል የማይባል መመቻመች የሚጠይቅ ነገር መሆኑ ላይ ነው፡፡
> የሚለው እምነት አሁንም ድረስ ሰፊ ቢሆንም ይህንን ሃሳብ የሚሞግቱ ሃሳቦች በአንፃሩ እየተጠናከሩ መጥተዋል፡፡ ይህንን ጥያቄ አብራርቶ ለመመለስ ጥልቅ ፍቅር እንዴት ያለ ነው? የሚለውን መረዳት ያስፈልጋል፡፡

የቅርብ ጊዜ የፍቅር እና ትዳር ትስስር

> የሚል ድምፅ ጎልቶ መደመጥ የጀመረው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ነው፡፡ ስቴፋኒ ኮንተዝ(2005) ‹‹ይህ እሳቤ ከሁለት ክፍለ ዘመን ወዲህ የመጣ ነው፡፡ ሰዎች ሁልጊዜ በፍቅር ይወድቁ ነበር፤ እርስ በእርሳቸው ከልብ ይፋቀሩ ነበር፤ ይሁን እንጂ ፍቅር ለመጋባት እንደ ቅድመ ሁኔታ ይቀመጥ የነበረው ከስንት አንዴ ነው›› ይላል፡፡ ኮንትዝ ቀጠል ያደርግናም እንዲህ ይላል ‹‹ፍቅር የትዳር የጎንዮሽ ተፈላጊ ውጤት እንጂ ወደ ትዳር መግቢያ ቅድመ ሁኔታ ተደርጎ በብዙ ባህሎች አይታሰብም ነበር››
በተመሳሳይ ሁኔታ ፓስካል ብሩክነር(2013) የሚከተለውን ይላል፡፡ ‹‹ትዳር በብዙ ባህሎች ውስጥ የተቀደሰ ትስስር መሆኑ ይታመናል፡፡ ከዚህ ውጭ ፍቅር ኋላ ላይ የሚመጣ ከሆነ እንደ አንድ ተጨማሪ ቦነስ ብቻ ይወስዳል፡፡ አሁን አሁን ግን ትዳር ለመመስረት ፍቅር ቅድመ ሁኔታ ሆኖ በመቀመጡ ከትዳር ይልቅ ፍቅር ቅዱስ ሆኗል፡፡ በምትኩ ትዳር ሁለተኛ ደረጃን እየያዘ ነው›› በዚህ ምክንያት በተለይ በምዕራቡ ዓለም የተጋቢዎች ቁጥር እየቀነሰ የመጣ ሲሆን የፍቺ እና ያለ አባት ወይም ያለ እናት የሚመሩ ጎጆዎች ቁጥርም በአንፃሩ እያሻቀበ ነው፡፡ ብሩክነር ከዚህ በተጨማሪ ፍቅር ከትዳር ይልቅ ቅድሚያ ቦታ እየተሰጠው ቢሆንም እውስጥ ሆኖ ግን አጥፍቶ እየጠፋ ያለ ይመስላል ይላል፡፡
ትዳር ለመመስረት የጦፈ ፈቅር ቅድመ ሁኔታ ሆኖ በመቀመጡ የትዳር ዋጋ ከፍ ብሏል፡፡ ይህም ትዳር የብዙዎች ቀዳሚ አጀንዳ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ይኸው አይነት ፍቅር መልሶ ትዳር መቅኖ ቢስ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ የጦፈ ፍቅር የለም በሚል ምክንያት ባለትዳሮች እና ጥንዶች መለያትን እንደ ሁነኛ አማራጭ ተያይዘውታል፡፡

ትስስሩን መቃወም

ፍቅርን እንደ ትዳር መሰረት ስናስብ ሁለት አይነት ተቃዋሚ ሃሳቦች ነፍስ ዘርተው ይነሳሉ፡፡
1. ትዳር ከፍቅር በተጨማሪ ሌሎች በርካታ ነገሮችን ግምት ውስጥ እያስገባን የምንኖርበት ማዕቀፍ ነው፡፡
2. የጦፈ ፍቅር አጭር ጊዜ ብቻ የሚቆይ በመሆኑ በረጅም የጊዜ ሂደት የሚመጡ የፍቅር ሌሎች ገፅታዎች ይበልጥ ግንዛቤ ውስጥ ሊገቡ ይገባል፡፡

የመጀመሪያው ሙግት ትዳር በአንድ አይነት ማህበረ ኢኮኖሚያዊ እና ባህላዊ ስርዓት ውስጥ የሚኖር ቁርኝት እንደመሆኑ መጠን የጥንዶቹ አጠቃላይ የደህንነት ይህንን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ባህላዊ ማዕቀፍ ግምት ውስጥ ያስገባ መሆን መቻል አለበት የሚል ነው፡፡ ሁለተኛው የመከራከሪያ ሀሳብ በሌላ በኩል የጦፈ የሚባለው ፍቅር አይነት ያልተረጋጋ፣ እና ለውስን ጊዜ ብቻ ደስታ የሚሰጥ መሆኑ ላይ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ለረጅም ጊዜ የተረጋጋ ህይወት ምንጭ ሊሆን ከሚችለው ትዳር ጋር ይጋጫል፡፡ እነዚህ ሁለት መከራከሪያ ሃሳቦች ሲጨመቁ ትዳር በሚመሰረትበት ወቅት ለፍቅር ብቻ ቅድሚያ የሚሰጥ ከሆነ መጨረሻው ‹‹ሲያልቅ አያምር›› ይሆናል የሚል ነው፡፡

ትዳር ከፍቅር ውጪ የሚያስገኛቸው ሌሎች በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ግልፅ ነው፡፡ በመሆኑም ትዳር ሲመሰረትም ሆኖ የመፍረስ አደጋ ሲያንዣብብበት እነዚህን ከጦፈ ፍቅር ውጪ የሚገኙ ተጨማሪ ሁኔታዎችንም ያገናዘበ መሆን አለበት፡፡ ለምሳሌ፣ ትዳር ሲመሰረት ጥንዶቹ በጋራም ሆነ በተናጠል ቤት ውስጥ የሚያስፈልጉ ነገሮችን ማሟላት እና ጥሩ ወላጅ መሆን መቻላቸው በቀዳሚነት ሊነሳ የሚችል ጉዳይ ነው፡፡ እውነትም በታሪክም ቢሆን ትዳር የጥንዶችን ጤናና ሀብት የሚያሻሽል ቢያንስ ቢያንስ እንኳን የማይጎዳ አብሮነት እንደሆነ ነው የሚታመነው፡፡ ለፍቅር ብቻ ሲሉ ትዳር መመስረት ግን ጥንዶቹ እነዚህን ተጨማሪ ገፅታዎች እንዳይመለከቱ ሊያደርጋቸው ይችላል፡፡ እንደውም እንዲህ የሚነበብ አባባል አለ፡፡ ‹‹ለጦፈ ፍቅር ብቻ ሲሉ የሚጋቡ ጥሩ ምሽቶችን እና መጥፎ ቀኖችን ያሳልፋሉ››

ትስስር መፍጠር
በፍቅር እና ትዳር መካከል ትስስር ለመፍጠር በጊዜያዊ የጦፈ ፍቅር ስሜት እና ዘለቄታ ባለው ጥልቅ ፍቅር መካከል ያለውን ልዩነት መገንዘብ ያሻል፡፡
ጥልቅ ፍቅር እንደ ጊዜያዊ የጦፈ የፍቅር ስሜት ለተወሰነ ጊዜ ያህል ብቻ የሚጎበኘንን ጠንካራ የመፈለግ ስሜት ብቻ ሳይሆን አመለካከታችንን እና ጠባያችንን ዘለቄታ ባለው መንገድ ይቃኛል፡፡ ጠንካራ የሆነ ስሜታዊ ወሲባዊ ፍላጎት ብልጭታ ለተወሰነ ጊዜ ውስጣችን ይቆይ ይሆናል፡፡ በአንፃሩ ጥልቅ ፍቅር ግን ያለማቋረጥ እያበራ ስሜታችንን ያሞቃል፣ ጠባያችንን ያንጻል እንዲሁም ከጊዜ እና ቦታ ጋር የሚኖረንን ቁርኝት መልክ መልክ ያስይዛል፡፡ የጦፈ የፍቅር ስሜት የሚያሳየው አጭር ጊጊ የሚቆይ የስሜት ኃያልነትን ብቻ ነው፡፡ በሌላ በኩል ጥልቅ ፍቅር ግን በረጅም የጊዜ ሂደት ውስጥ የሚፈጠርን፣ በሁሉም መልኩ የሚያበራን፣ የሁለቱንም ጥንዶች ህይወት እንዲያብብ እና እንዲያፈራ የሚያደርግ ፍቅር ነው፡፡ ጥልቅ የሆነ የፍቅር ህይወት ጥብቅ ከሆነ ጊዜያዊ ስሜት የተለየ ነው፡፡ የአፍታ ወሲባዊ ፍላጎት ከዘመናት የፍቅር ህይወት በላይ ጥብቅ ሊሆን ይችላል፡፡ ይሁን እንጂ ጥልቀቱ እዘህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡

ለጦፈ ፍቅር ብቻ ሲባል ትዳር መመስረት በ3 ምክንያት ብልህ ውሳኔ አይደለም፡፡
1. ፍቅር የሚለዋወጥ ስሜት ነው፡፡
2. ፍቅር ብቻውን ጠንካራ መሰረት ሊሆን አይችልም፡፡
3. ከፍቅር በተጨማሪ ሌሎች በርካታ ነገሮች ያስፈልጉናል፡፡
የአንድን ሰው እንበልና አዕምሮአዊ ብቃቱን ወይም ደግነቱን ግምት ውስጥ ሳያስገቡ ትዳር መመስረት ለጊዜው አፍቃሪ ውሳኔ ሊመስል ይችላል፡፡ ነገር ግን በረጅም ጊዜ አብሮነት ውስጥ ዋጋ ባላቸው ማገናዘቢያዎች ሲፈተሽ ግን አስፈሪ ውሳኔ መሆኑ ግልፅ ይሆናል፡፡
ትዳር ለመመስረት በምንነሳበት ወቅት ፍቅር ቦታ ሊኖው ይገባል፡፡ ይሁን እንጂ የዛሬም ሆነ የወደፊት ህይወት ደስታ እና ትርጉም ጊዜዊ የጦፈ የፍቅር ስሜት ላይ ብቻ ሊመሰረት አይገባም፡፡ ይልቁንም መተሳሰብን፣ መመሳሰልን፣ መጋራትን፣ እና በመጠኑም ቢሆን ስሜታዊ መፈላለግን መሰረት ያደረገ ጥልቀት ያለው ፈቅር ላይ ሊደገፍ ይገባል፡፡ ስኬታማ ትዳር ከአንድ ሰው ጋር ደግሞ ደጋግሞ በፍቅር መውደቅን ይጠይቃል፡፡
ቸር እንሰንብት፡፡

እንጦጦ አካባቢ አንድ የከተማ አውቶብስ በሰባት ሰዎች ላይ የሞት አደጋ አደረሰ

0
0

ከእንጦጦ ኪዳነ ምህረት ወደ ሺሮ ሜዳ ሲጓዝ የነበረ የከተማ አውቶብስ በሰባት ሰዎች ላይ የሞት አደጋ አደረሰ።
entoto
እንጦጦ ኪዳነ ምህረት አካባቢ ትናንት ምሽት 2 ስአት ከ25 ላይ ነው አደጋው የደረሰው።

በአደጋው ሶስት ሶስት ሰዎች ወዲያውኑ ህይዎታቸው ሲያልፍ ሶስቱ ደግም ወደ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ ሊደረግላቸው ሲል መንገድ ላይ አርፈዋል። አንደኛው ደግሞ ዛሬ ጠዋት ላይ ህይወቱ አልፏል።

በአደጋው ህይዎታቸው ያለፈው ሁሉም መንገደኞች ሲሆኑ፥ የአደጋው መንስኤም በመጣራት ላይ ይገኛል ተብሏል።

በርካታ ሰዎች ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑም ተገልጿል።

አውቶብሱ ከኤሌክትሪክ ምሰሶ ጋር ተጋጭቶ ስለነበር የድንገተኛ አደጋ ቁጥጥሩን አስቸጋሪ አድርጎት እንደነበርም ተነግሯል።

ምንጭ፦ ፋና ኤቢሲ

የመከላከያ ሰራዊት አባላት ለመለስ ፋውንዴሽን ገንዘብ እንዲያዋጡ መጠየቃቸውን ተቃወሙ

0
0

7928383556_e809223ebdነሃሴ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የመከላከያ ምንጮች እንደገለጹት የሰራዊቱ አባላት ለመለስ ፋውንዴሽን ገንዘብ እንዲያዋጡ በተጠየቁበት ወቅት ተቃውሞ
አሰምተዋል። በባድሜ አካባቢ የሰፈሩት የመከላከያ አባላት በደሞዝ ክፍያ ሳምንት መነሻው 200 ብር ሆኖ በየደረጃው ያሉ ወታደሮች እንደ ማእረጋቸውና ደሞዝ መጠናቸው
እንዲከፍሉ ሲጠየቁ፣ የሰራዊቱ አባላት ደሞዛችን አይቆረጥም በማለት ተቃውሞ አሰምተዋል።

ደሞዝ ከፋዮቹ ከላይ የመጣ መመሪያ ነው በሚል ሊያግባቡዋቸው ቢሞክሩም የሰራዊቱ አባላት ፈቃደኞች ሳይሆኑ ቀርተዋል። አንድ የ3ኛ ሻለቃ አንደኛ ጋንታ አባል የሆነ ወታደር
አመጹን መርተሃል ተብሎ ሊታሰር ሲል አምልጦ እስከነመሳሪያው ተከዜ ውስጥ ገብቶ መሞቱ ታውቋል። ይህንን ተከትሎ መጠናኛ ብጥብጥ መነሳቱን ምንጮች አክለው ገልጸዋል።
በአሁኑ ሰአት ውጥረቱ እንዳለ ሲሆን፣ ከመከላከያ እየጠፉ የሚሄዱትም ቁጥራቸው እየጨመረ ነው።

ባለፉት 3 ቀናት መከላከያን ጥሎ የጠፋ አንድ ወታደር እንደገለጸው፣ ሰራዊቱ በከፍተኛ ምሬት ውስጥ እንደሚገኝና የሚከዳው ሰራዊት ቁጥርም ከፍተኛ መሆኑን ተናግሯል። በተከዜ
አካባቢ በሚካሄደው የኮንትሮባንድ ንግድ የአንድ አካባቢ ሰዎች የሆኑ የመከላከያ አዛዦች እየተጠቀሙ ነው የሚለው አባሉ፣ ከእነሱ ውጭ ያለው የመከላከያ አባል በችጋር እየተጠበሰ
ባለበት ወቅት ለመለስ ፋውንዴሽን በሚል እንደገና መዋጮ መጠየቁ ብዙዎችን ስሜት የረበሸ ሆኗል ብሎአል።

እነሱ ተጨማሪ ገቢ አላቸው፣ እኛ ግን የምትሰጠንን ደሞዝ እንኳ ቆጥበን ለቤተሰቦቻችን እንዳንረዳ በመዋጮ እና በሰበብ አስባብ ይወስዱብናል ሲል ተናግሯል።
በኢትዮጵያ በወታደራዊ አዛዦችና በተራው ሰራዊት መካከል ከፍተኛ የሆነ የኑሮ ልዩነት አለ። አብዛኞቹ የመከላከያ መኮንኖች የህወሃት አባላት ሲሆኑ፣ በአዲስ አበባ እና በኢትዮጵያ
ዋና ዋና ከተሞች ዘመናዊ ቪላዎችንና ፎቆችን ሰርተው በወር በመቶሺዎች የሚቆጠር የኪራይ ገቢ ያገኛሉ። በአገሪቱ ውስጥ የሚካሄደውን የኮንትሮባንድ ንግድ የሚያስፈጽሙት፣
በመከላከያ ስም ያለቀረጥ የሚያስገቡዋቸውን እቃዎች በርካሽ በመሸጥ ህጋዊዎቹን ነጋዴዎች እያከሰሩ ከስራ ውጭ እያደረጉዋቸው መሆኑን በርካታ ነጋዴዎች ለኢሳት ይናገራሉ።

  1. Source: Ethsat

ዓባይ እንደዋዛ፤ የግብፆች “ተፈጥሯዊና ታሪካዊ መብት” ክስተቶች ክፍል አምስት (አክሎግ ቢራራ)

0
0
Dr. Aklog Birara

Dr. Aklog Birara

አክሎግ ቢራራ (ዶር) የዛሬዋ ኢትዮጵያ ባለቤት አላት ለማለት አያስደፍርም። የህወሓት/ኢህአዴግ ሕገ-መንግሥት ኢትዮጵያ የምትባለ ረጂም ታሪክ ያላላት እንዳትሆን ከስሯ አናግቷታል። ሉዓላዊነት ከኢትዮጵያ ተዘዋውሮ በቋንቋ ለተደራጁ አዲስ መሳፍንት ለሆኑ የክልል አለቃዎች ተሰጥቷል። ህወሓት/ኢህ አዴግ ይኼን ያደረገበት ስትራተጂካዊ ምክንያት የታወቀ ነው፤ ከፋፍሎ ለመገዛት እንዲያመች። አስቸጋሪ ሆነ የምናየው ተቃዋሚው ክፍል ባለቤትነት ለመያዝና አገሪቱን ለመታደግ ብቁነት አለማሳየቱ ነው። ሻቢያ፤ ህወሕትና ሌሎች የጎሳ ስብስቦች አገሪቱን ለድርድር አቅርበው እንደ ሸቀጥ ቸርችረው የባህር በሯን ከዘጉ በኋላ አሁንም ልዩ ልዩ ክፍሎች ካለፈው አልተማሩም ለማለት ይቻላል። ዛሬም እንደ ዱሮው፤ ኢትዮጵያ በገዢው ፓርቲና በአንዳንድ ስብስቦች ለድርድር ታጭታ ትገኛለች። በ60ዎቹና በ70ዎቹ መጀመሪያ ለሃገራቸው ልማትና ለዲሞክራሲ—   [ሙሉውንለማንበብእዚህላይይጫኑ]—-

የህብረቱ ሂደትና የውህደት ጥያቄ (ኢትዮ ለጋ)


በባህር ዳር ከተማ ተደርጎ በነበረው ስብሰባ ላይ የኢህአዴግ ተወካዮች ምሬታቸውን ገለጹ (ከአስግድ ታመነ)

0
0

f0c3a021df8a28f4e3936660c10f3aba_L

በባህርዳር ከተማ ተደርጎ በነበረው ስብሰባ ላይ የምክር ቤት አባላት ፣” የህዝብ ወኪሎች ብንሆንም ስራ አስፈጻሚው አካል የምናቀርበውን ሪፖርት አይቀበልም” ብለዋል። አንድ ኢንቨስተር ከአንድ የህዝብ ተመራጭ የተሻለ ተሰሚነት አለው ያሉት ተማራጮች መፍትሄ ለማምጣት ካልቻልን የእኛ ተመራጭነት ምንድነው ሲሉ የምክር ቤት አባላት ጥያቄ አቅርበዋል audio ( 00-01፡54)
የህዝብ ተወካዮቹ እንደገለጹት በአሁኑ ጊዜ በፍድር ቤቶች አካባቢ ከፍተኛ ችግር እንዳለም ገልጸዋል። አንድ ተወካይ የመንግስት ሆስፒታሎች እየተዳከሙና መድሃኒቶች እየተሸጡ፣ ህዝቡም ከመንግስት የጤና ተቋማት ይልቅ ወደ ግል እየሄዱ መሆኑን ገልጸዋል።
ህብረተሰባችን ምን ላይ ነው ያለውን የማጥናት ችግር አለ ያሉት ሌላው ተወካይ፣ በምዞርባቸው ቦታዎች ሁሉ ህዝቡ መውደቂያ አጣን ብሎ እንደሚጮህ ተናግረዋል። 
ኢህአዴግ ለመጪው ምርጫ ዝግጅት በሚመስል መልኩ በተለያዩ ደረጃ የሚገኙ የህዝብ ተወካይ የሚላቸውን ሰዎች እየጠራ በማወያየት ላይ ነው።እስካሁን ድረስ በተደረጉት ውይይቶች አብዛኛው ተወያይ በአገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ ሆነ የኢኮኖሚ ና የአስተዳደር ችግሮች እንዳሉ በድፍረት መግለጹን ኢሳት ሲዘግብ መቆየቱ ይተወቃል።

የኢትዮጵያውያን የስፓርትና ባህል ፌዴሬሽን 12ኛው ዓመታዊ በዓል በምዩኒክ ከተማ ጀርመን ተጠናቀቀ

0
0
MUNICH 2014 ESCFE Festival  Photo courtesy of escfe.net

MUNICH 2014 ESCFE Festival
Photo courtesy of escfe.net

የኢትዮጵያውያን የስፓርትና ባህል ፌዴሬሽን 12ኛው ዓመታዊ በዓል በምዩኒክ ከተማ ጀርመን ክጁላይ 30 ቀን 2014 ዓ..ም. እስከ ኦገሰት 2 ቀን 2014 ዓ.ም በፕሮግራሙ መሰረት ተካሂዶ ተጠናቁኣል፡፡የተለያዩ ስፖርታዊ ዝግጅቶች የአዋቂዎች 25 ቡደኖች ሲዘጋጁ 18ቱ በ1ኛ ዲቪዚዮንና ሰባቱ ደግሞ በ2ኛ ድቪዚዮን ሲመደቡ፤ በ1ኛው ድቪዚዮን 25ቱ ቡደኖች በአራት ግሩፕ እንዲከፈሉ ተደርገዋል፡፡ በሁለተኛው ድቪዚዮን ሰባቱ ቡድኖች በሁለት ግሩፕ ሆነው ተዘጋጅተዋል፡፡ሁለት ቡድኖች እንዳልመጡና እነርሱም ስዊድንና ኢትዮ ፍራንስ መሆናችው ተነግሯል፡፡ የማጣሪያውን ወድድር ከ1ኛው ድቪዚዮን 8 ቡድኖች ሲያልፉ፤ ክ2ኛው ድቪዚዮን 4 ቡድኖች አልፈዋል፡፡ በጥሎ ማለፉ ጨዋታ ከስምንቱ ቡድኖቸ ለመጨረሻው የዋንጫ ጨዋታ ኢትዮ ኖርዌይና ኢትዮ ለንደን ተቃዋሚዎቻቸውን በማሽነፍ አልፈዋል፡፡ከሁለተኛው ደቪዚዮን ኢትዮ ምዩኒክ 96 ና ኢትዮ ሸቱትጋርት ተቃዋሚቻችውን አሸንፈው ለመጨረሻው የዋንጫ ጨዋታ አልፈዋል፡፡በመጨረሻም ኢትዮ ለንደን ከኢትዮ ኖርዌይ ጋር ተጫውተው ኢትዮ ለንደን 2 ለ 1 ውጤት የ12ኛውን ዓመት የኢትዮጵያውያን የአውሮፓ የስፖርትና ባህል ፌዴሬሽን  አሽናፊ ሆኗል፡፡ ከሁለተኛው ድቪዚዮን በኢትዮ ሽቱትጋርትና ኢትዮ ምዩኒክ 96 በተደረገው የዋንጫ ጨዋታ ኢትዮ ሽቱትጋርት አሸንፎ የ2014 ዓመት  የሁለተኛው ድቭዚዮን ውድድር አሽናፊ ሆኗል፡፡ የታዳጊ ወጣቶች የእግር ኩኣስ ውድድር በቂ ግዜ ተስጥቶት ከዚህ በፊት ከነበረው በተሻለ መንገድ ተከናውኗል፡፡ኢትዮ ስዊዘርላንድና ኢትዮ ኢሚሊያ ታዳጋዎች ብዙ ተስፋ የሚጣልባቸው እንደሆኑ በሜዳው ላይ በተግባር አስመስክረዋል፡፡ይህንን በጣም ከባድና አስቸጋሪ ዝግጅት በማቀናበር ለተሳተፉት አስልጣኞች ዝቅ ብለን ከልብ የሆነ ምስጋናችን ይድረሳችሁ እንላለን፡፡ለታዳጊ ወጣቶች አሽናፊዎችም የዋንጫና የሜዳልያን የኩኣስ ሽልማቶች በተገቢው መንገድ ከፌዴሬሽኑ ባልስልጣናት ተስጥቷቸዋል፡፡ሌሎችም አካባቢዎች በዚህ ደረጃ ተዘጋጅተው ለሚቀጥለው ዓመት ውድድር የታዳጊ ወጣቶችን ቡድኖች አዘጋጅተው እንዲቅርቡ ጥሪ እናደርጋለን፡፡ በስፖርቱ መስክ የሴቶች እህቶቻችንና እናቶቻችን ተሳትፎ እንዲጨምር ሴቶች እራሳቸው ጥረት በማድረግ ካሁኑ ዓመት የተሻለ ሁኔታ ቢፈጥሩ የተሻለ ይሆናል፡፡ባሁኑ ዓመት የኢትዮ ምዩኒክ የቮሊቮል ቡድን በብቸኝነት ቀርቦ ተወዳዳሪ በማጣት ብቸኛው ተወዳዳሪና አሸናፊ በመሆን የሜዳሊያ ሽልማት ተደርጎላቸዋል፡፡ ለሚቀጥለው ዓመት ውድድር በተወዳዳሪነት እንደሚቀርቡ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ 5 ኢትዮጵያውያን የእግር ኩአስ ዳኞች ጠቅላላ የእግር ኩኣስ ውድድሮችን በታዛቢነት በሶስቱም ሜዳዎች በመሆን ፌዴሬሽኑ እየመደባቸው እስከ መጨረሻው ድረስ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ እነዚህ 5 ኢትዮጵያውያን ዳኞች የነበራቸው ሃላፊነት አንድ ጨዋታ ሲደረግ የሚጫወቱበት ሜዳ ላይ በመገኘት የሁለቱንም ቡድኖች የተጨዋቾች መታወቂያ እያንዳንዱን ተጨዋች እሱ መሆን አለመሆኑን ማረጋግጥ ሲሆን ይህን ያላሟላ ተጨዋች አይጫወትም፡፡ ተጨዋች ሲለወጥ የሚለወጠውን ተጨዋች ማንንት ማረጋገጥና ለረዳት ዳኛው በሚቀጥለው የጨዋታ መቁኣረጥ ልውውጥ እንዳለ ማሳወቅና እንዲቀየር ማድረግ፤ በጨዋታው ወቅት ያለውን ሁኔታ መዘግብ ለምሳሌ ጎሎችን፥ ቢጫ፥ ቢጫና ቀይና ቀይ ካርድ መጻፍ፥ ሌሎች ሁኔታዎች ከተከሰቱም ጽፎ በመጨረሻ ለፌዴሬሽኑ ሃላፊ ማቅረብ ናቸው።የታዳጊ ወጣቶችን፥ የሸማግሌዎች ቡድንና የሁለተኛ ዲቪዝዮን የመጨረሻ የዋንጫ ጨዋታ በኢትዮጵያውያን ዳኞች ተመርቷል፡፡ የኢትዮጵያውያን ዳኞች እንዳይገኙ አዘጋጁ የኢትዮ ምዩኒክ ቡድን ፍላጎት ሰለነበረ፥ ፌዴሪሽኑ ከኢትዮጵያውያን ዳኞች ጋር ብዙ የስልከ ግነኙነቶች በማድረግ፥ በተለይም በቴክኒክ ኮሚቴ ሃላፊው ጥረት እንዲገኙ እንደተደረገ ነው ፡፡

የዝግጅቱቦታ

የዝግጅቱ ቦታ በጣም አመቺ ሲሆን በተለይ ለህፃናት ብዙ የሚመች ነው፡፡የእግር ኩኣስ ሜዳዎቹ ሶስት ሲሆኑ ሶስቱም መብራት ዬላቸውም፡፡ አንዱ ሜዳ ቢያንስ መብራት ቢኖረው ችግር ቢያጋጥምና ቢመሽ በመብራት መጫወት የሚቻልበትን ሁኒታ አመቺ ያደርጋል፡፡ወደፊት የሚያዘጋጀው ቡድን ይህንን  ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው ነጥብ ነው፡፡ለነጋዴዎች ብዙ ትናንሽና ትላልቅ ድንኩኣኖች  በመትከል የተለያዩ አገራዊ ምግቦች በ€10 ለተመጋቢዎች ቀርበዋል፡፡ለስላሳ መጠጥ €3 ነበር፡፡ እኔን የምዩኒክ ባህል የሚለው ድንኩኣን ውስጥ የሚሽጠው ደረቅ ጥብስ በእንጀራ ከአዋዜ ጋር ቁኣሚ ምርኮኛ አድርጎኛል፡፡የኢሳት ድንኩኣን ውስጥም „ኢሳት የኢትዮጵያውያን ጆሮ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር“ የሚል ማሰታወቂያ በተደጋጋሚ ያስማ እንደነበር ነው፡፡የተለያዩ አረንጉኣዴ ቢጫ ቀይ ቀለም ያላቸው ጌጣጌጦች፥ሹራቦች፥ ቀሚሶች፥…ወዘተ ለሽያጭ በየድንኩኣኖቹ ቀርበዋል፡፡ የኢትዮጵያን ባንዲራ ቀለም ጫማ ላይ መደረጉን ያዩና ያስቆጣቸው ሰዎች ነበሩ፡፡ይሄ ለወደፊቱ ቢታስብበት መልካም ነው፡፡ ከድንኩኣኖቹ መሃከል የተለያዩ ዝግጅቶች የቀረቡብት ዋናው መድረክ ላይ የወያኔው ቀኝ እጅ የሆነው  አቶ እስጢፋኖስ ወይም በሌላ ስሙ ጂሚ የሚባለው የኮሎኝ ከተማ ነዋሪ የሆነው የወያኔን ፖለቲካ የእሱን ግሩፖች ጀርመኖችና ሌሎችንም በማቅረብ ፕሮፓጋንዳውን በብቸኝነት እንዲያካሂድ መደረጉ የአዘጋጁን የፖለቲካ ወገንተኝነቱን ያሳያል፡፡የተሻለ የሚሆነው ለሁለቱም ወገኖች ማለትም ለወያኔ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች እኩል ግዜና መድረክ ለየብቻቸው መስጠት ወይም ሁለቱንም ወገኖች መድረክ አለመስጠት ነው፡፡ በተለያዩ ድንኩአኖች ቡና፥ ኤስፐሬሶ፥ አሳምቡሳና ለልጆች የተጠበሰ ድንችና ሌሎች ለስፖርቱ እንግዶች በአማራጭነት ቀርበዋል፡፡ወደ ሁዋላ ለየት ብለው የሚገኙ ድንኩአኖችን ጠጋ ብሎ ለተመለክተ በጣም አሳዛኝና አደገኛ የሆኑ ሸቀጦች የሚሸጡብት ሰፍራ ነበር፡፡ ጫት የሚታኘከበትና የሚሽጥበት፥ ሺሻ የሚሳብበትና ሌሎች አድንዛዥ እፆች ሰፈር ነበር፡፡ይህ ሁኔታ የአዘጋጁ የኢትዮ ምዩኒክ ስምምነት ተግባራዊ ሊሆን ስለማይችል፤ በዚህ ነጥብ ያለ ምንም ይቅርታ መወገዝ ያለበት ነው፡፡ ለታዳጊ ወጣቶች ስለጫት ሽያጭና መቃም፥ሺሻ እንዴት መሳብ እንዳለብትና ከሌሎች አደንዛዥ እፆች ጋር ለማስተዋወቅ ካልሆነ በስተቀር፤ ይህ ዓይነቱ ድርጊት አስመልክቶ ኢትዮ ምዩኒክ በሰራው ጥሩ ስራ እንደተመሰገነው በዚህ ፀረ ስፖርት ድርጊት መወገዝ ያለበት ነው፡፡ፌዴሬሽኑም የዚህ ዓይነት ፀረ ስፖርት ድርጊቶች አዘጋጁ አገር አስተማማኘ በሆነ መልኩ ተግባራዊ እንዳያረግና ከልከል መሆኑን ማሳወቅና ይህንን የማያሙኣላ ቡድን ከፌዴሬሽኑ ሊወገድ የሚችልበትን ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ ይኖርበታል፡፡አዘጋጁ ቡድን ላለበት አገር ፖሊሶች ዝግጀት እንዲያደርጉ በቅድሚያ ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡

 የኢትዮምዪኒክናኢትዮሆላንድጨዋታ

በኢትዮ ምዪኒክና ኢትዮ ሆላንድ መሃከል የእርስ በርስ መማታት ሁኔታ ተፈጥሮ ሶስቱ ጀርመናዊ ዳኞች ጨዋውን አቁኣርጠው ሄደዋል፡፡ከዚያም በፊት አንድ የኢትዮ ምዩኒክ ተቀይሮ ከወጣ በሁላ አጨዋቹን ዳኛ በመስደቡ ቀይ ካርድ ሲሰጥወ፥ ዳኛውን „ሰምህ ማነው? ከጨዋታ በሁኣላ እገኘሃለሁ“ በማለት ካሰፈራራው በሁኣላ አጨዋቹ ዳኛ „ኣራት ደቂቃ እሰጠሃለሁ፡፡ ከሜዳው ከልል ውጭ ካልሄድክ ጨዋታወን አቁኣረጣለሁ“ ካለው በሁኣላ በመሪዎቹ ገፋፋኒት ሜዳውን ጥሎ እንድሄድ ተደርጉኣል፡፡ከዚያ ጨዋታው በኢትዮጵያዊው ዳኛ የቀረው የጨዋታ ሰዓት እንዲያልቅ ተደርጉኣል፡፡ይሀ ዓይነቱ አስራር ትክክል ሰላልሆነ ለወደፊቱ ሊሻሻል ይገባል፡፡ምከንያቱም  ጀርመንያዊ ዳኛ ጨዋታውን ያቁኣረጠበትን ምክንያት ለፌዲዲሪሽኑ ማሳወቅና ለጨዋታው መቁኣረጥ ምክንያት አንድ ቡድን በቻ መሆኑን ወይም ሁለቱም ቡድኖች መሆናቸውን በግልጽ ሊያስቀምጥ ይገባል፡፡ፌዴሬሽኑ ውሳኒውን ዳኛው በሰጠው መረጃ መሰረት አድርጎ ለጨዋታው መቁኣረጥ ምከንያት አንድ ቡድን ከሆነ፤ ይህንን ቡድን 3 ለ 0 ተሽናፊ እንዲሆን ማድረግ፤ ሁለቱም ቡድኖች ለጨዋታው መቁኣረጥ ምክንያት ከሆኑ ደግሞ ሁለቱም ቡድኖች 0 0 ነጥብ እንዲኖራቸው ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ጨዋታው በምንም መልኩ ሊቀጥል አይገባውም፡፡ይሄ ጥፋተኛውን  ውይም ጥፋተኞችን በተዘዋዋሪ የተስራውን መጥፎ ድርጊት ማበረታታት ይሆናል፡፡ባይገርማችሁ አንድ ወጣት ልጅ አጠገቤ ቆሞ ሲደባድቡ እያየ „እንዴ ትላልቅ ስዎችም ይደባደባሉ ?“ በማለት ሲገረም አድምጫለሁ፡፡የዛሬው አልፏል፡፡ ለወደፊቱ ፌዴሬሽኑ ሊያሰብበት ይገባል፡፡

የታዳጊወጣቶችየቅጣትምትሁኔታ

ዋታው የጥሎ ማለፍ ውድድር ስለሆነና እኩል ለእኩል ስለወጡ፤ አሽናፊውን በቅጣት ምት ለመለየት ተራ በተራ የኢትዮ ፓርሚሊ ከኢጣሊያና የኢትዮ ስዊዝ ቡድኖች ተጨዋቾች ቅጣት ምት ይመቱ ነበር፡፡ በጣም የሚገርመው ከሁለቱም በኩል ያሉት በእድሜ አንጋፋ ከሆኑት ተጨዋቾች የተሻለ የአመታት ችሎታ የነበራቸው ታዳጊ ወጣቶች ነበሩ፡፡ምሰጋናው በማያሻማ መልኩ ለአስልጣኞቻቸው የሚስጥ ነው፡፡በርቱ በርቱ ያስኛል፡፡ ታዲያ ጥሩ ጥሩ የሚባሉት ሁልግዜ በቅድሚያ የሚመቱት ሲሆኑ፥ ቅጣት ምቱ እኩል ለእኩል በመሆን ለረጅም ደቂቃዎች ስለቀጠለ ጎበዝ የሚባሉት መትተው ሌሎቹም ተራ በተራ መምታት ነበረባቸው፡፡አንድ እናትና አባት አካባብዬ ነበሩ፡፡“ውይ እሱ እንዳይመጣ ብቻ እኔ አላይም፡፡ቅጣት ምቱን የሳተ እንደሆነ በጣም ስለሚናደድ እሱም አይተኛም፡፡ እኛንም አያስተኛንም፡፡“ ስትል አያገባም ያለችው ልጃቸው ተራው ደረስና ሮጣ ላለማየት ሄደች፡፡ አባትዬወም ዓይኑን ወደሌላ እቅጣጫ አዞረ፡፡ እኔ ልጃቸው የፍጹም ቅጣት ሲመታ አየሁና ማግባቱን ነገርኩኣቸው፡፡እንዲያውም የጣሊያኑ ቡድን ልጃችው ያለበት በአሽናፊነት ለሚቀጥለው ውድድር አለፈ፡፡በማግስቱ ባልና ሚስቶቹን እግኝቼአቸው ስለነበር፤ ደህና መተኛታቸውን ጠይኩኣቸው፡፡ ሁለቱም ከት ብለው በመሳቅ በሰላም መተኛታችውን አረጋገጡልኘ፡፡ይሀም የሚያሳየው ወላጆቹም ምን ያህል አብረው እንደሚጨነቁ አንዱን ምሳሌ ለመጥቀስ ያህል ነው፡፡

መብረቅናጨዋታማቁኣረጥ

አንድ መሰረታዊ የሆነ ስህተት በሕፃናት የመጨረሻው የዋንጫ ውድድር ወቅት ተፈጽሟል፡፡ይኸውም ዝናብና የመብረቅ አደጋ በነበረበት አጨዋቹ ዳኛ ጨዋታውን ማቁኣረጥ ሲገባው መቀጠሉና ዳኛው እንኩኣ ቢሳሳት የፌዴሬሽኑ መናገሪያው ውስጥ የነበሩት አባላት ለዳኛ ጨዋታውን እንዲያቆም መንገሩ አስፈላጊ ነበር፡፡ አሁን ሁኔታው ምንም ዓይነት አደጋ ስላልደረስ እስየው በማለት ለወደፊቱ ፌዴሬሽኑ ለሁሉም ዳኞች የዚህ የመብረቅ አደጋ ሁኒታ ሲከሰት ጨዋታውን እንዲያቁኣርጡ በመመሪያ መልክ ተዘጋጅቶ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡እዚህ ላይ ወሳኙ ዳኛው በቻ ሊሆን ይገባል፡፡ የተለያዩችግሮች  

ለቡድኖችየሚጠጣውሃእቅርቦት

አዘጋጁ አገር ለቡድኖች የሚጠጣ ውሃ በየቀኑ ተመጣጣኝ የሆነ የውሃ እቅርቦት  ከዚሀ በፊት በቀጣይነት ይደረግ እንደነበርና በምዩኒክ በዓል ላይ ግን በተገቢው መንገድ እንዳልተሟላ ነው፡፡አያንዳንዱ ቡድን ጨዋታውን እስከጨረሰ ድረስ የሚጠጣ ውሃ አቅርቦት የአዘጋጁ የኢትዮ ምዩኒክ ሃላፊነት ሆኖ ሳለ በተገቢው ተግባራዊ ባለመደረጉ ቅሬታዎች ተስንዝረዋል፡፡ይህ በጣም ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ስለሆነ ፌዴሬሽኑም ይሀ ጉዳይ መሙኣላቱን ማረጋግጥ ይኖርበታል፡፡

የቁልፍበዛትማነስ

የተጨዋቾች መልበሻ ቤት ቁልፍ አለመኖር፤ የፌዴሬሽኑ ቢሮ ራሱን የቻለ ቁልፍ አለመኖር ችግር እንደፈጠረ ታይቷል፡፡

ኖራለመቀባት

የቁጥር ሜዳ 1 ኖራ ለማስቀባት ብዙም ትኩረት እንዳልተስጠውና ዳኞች መጥተው ሜዳውን ካዩ በሁኣላ በዚያ ሁኔታ የስምንት ቡድኖችን የማጣሪያ ውድድር ለማጫወት እንደማይችሉ ካሰታወቁ በሁኣላ የሚቀባውን ሰው ፍለጋ መራወጥ ተጀመረ፡፡ ከተባለው ሰዓት በጣም ዘግይቶ ቀቢው ሰውየው መጥቶ ሜዳውን ከቀባ በሁኣላ ጨዋታዎቹ ተካሂደዋል፡፡ከዚህ የምንማረው ትምሀርት ሜዳውን ለመቀባት የሚያሰችል ሁኔታ ዝግጅት አስፈላጊ እንደሆነና ወዲያው መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ማዘጋጀት ተገቢ እንደሆነ ነው፡፡ሁለተኛው አማራጭ ኖራው በድንብ ባልተቀባባት ሜዳ ላይ ለማጫወት 14 የሚተከሉ ባንዲራዎች ወይም በፕላስቲክ የሚስሩ ምልክቶች ማዘጋጀት ነው፡፡ ይህ የመጨረሻው አማራጭ ነው፡፡

የጀርመኖችዳኞች

የጀርመኖች ዳኞች በመጀመሪያው የማጣሪያ ውድድር ላይ ከነበሩት ብዙዎች ጥሩ አልነበሩም፡፡በተለይ ረዳት ዳኞቹ ለስም የነበሩ ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ መሃል ዳኞቹ ሜዳ 1ና 2 የነበሩት በአብዛኛው ጥሩ ዳኞች ነበሩ፡፡ በሜዳ 3 ላይ በማጣሪያው ውድድር ላይ የነበሩት ዋና ዳኞችም ሆኑ ረዳቶቹም በአብዛኛው ጥሩ አልነበሩም፡፡ክጥሎ ማለፍ ውደድሩ ጀምሮ አስከ ፍፃሜው ጨዋታ ድረስ የዳኙት ዳኞችም ሆኑ ረዳቶቹ ጥሩ ነበሩ፡፡ አንድ ጨዋታ ላይ ግን በማጣሪያ ውድድር ወቅት የመጀመሪያውን ግማሽ ግዜ ጨዋታ በሶስት ዳኞች ተመርቶ እረፍት ከተደረገ በሁኣላ  ሁለቱ ዳኞች ወዴት እንደሄዱ ሳይታወቅ ተሰወሩ፡፡ በጣም ብዙ ደቂቃዎች ከቆዩ በሁኣላ ተመለሱ፡፡ዋናው ዳኛ ግን ያለሁለቱ ዳኞች ጨዋታውን ቀጥሏል፡፡ይሀ እነዚህን ዳኞች በጣም የሚያስተች ሲሆን፥ ዋናው ዳኛም እነርሱን ይዞ የመቅረብ ሃላፊነቱን ባለመወጣቱ ሶስቱም ጀርመናዊ ዳኞች የስሩት ሰራ ትክክል አይደለም፡፡

ኩኣሶች

ኩኣሶች በብዛት ስለሚወስዱ ዳኞችና ታዛቢዎቹ ሁለት ሁለት ኩኣስ ለአንድ ሜዳ ይዘው ቢቀርቡና ጨዋታው ሲያልቅ ለፌዴሬሽኑ ተዋካዮች ኩኣሶቹን ቢያስረክቡ ብዙ ኩኣሶች ሊወስዱ አይችሉም፡፡በተጨማሪ ፌዴሬሽኑ የራሱ የሆን አንድ መንፊያ ቢኖረው መልካም ነው፡፡

ግርማሳህሌናማይክራፎን

የፌዴሪሽኑ ሰራ አስኪያጅ ኮሚቴ አባል የሆነው የኢትዮ ፓሪስ መሪ የነበረው አቶ ግርማ ሳህሌ ማይኩን መቼ ነው የሚለቀው ፥ ለሌላ ሰውስ የሚያቀብለው በማለት ፓልቶክ ቢሆን ቢያንስ ቀይ ከባሰም ባውንስ ሊደረግ እንደሚችል ሲዘባበቱበት ተደምጧል፡፡በዚህም አስታከው ማይኩን ና ሃላፊነቱንም ለሌሎች ቢያስረክብ ሸጋ መሆኑንም እነዚህ ወጣት ጠቅ ጠቅ አድራጊዎች  አልሸሸጉም፡፡ይሀንን ሲሉ ሌሎችንም ለረጅም ግዜ በተለያየ ሃላፊነት ላይ ያሉትንም ስም ሳይጠቅሱ ጎንተል አድርገዋል፡፡

ተጋባዥእንግዶች

ተጋባዥ እንግዶች በምን መልክ እንድሚጋበዙ ግልጽ በሆነ መልክ እንዳልተቀመጠና በጉኣደኝነት እንደሆነ ተደርጎ ሲተች ተደምጧል፡፡ይሀ ትችት ባሁኑ በዓል ላይ የተጋብዙትን ፈጽሞ የሚቃወም አይደለም፡፡ሰለዚህ ሁኔታ ፌዴሬሽኑ እንዴት አንድ ሰው በእንግዳነት እንደሚምረጥ ለማንም ሰው ግልጽ በሆነ መልኩ በጽሁፍ ማብራሪያ ቢሰጥበት ጥርጣሬዎችና አሉባልታዎች ብዙ ቦታ አያገኙም፡፡

የፌዴሬሽኑገቢናወጪምርመራሪፖርትጉዳይ

የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌዴሬሽን ነኝ ብሎ የሚንቀሳቀስ ከሆነ፥ የፌዴሬሽኑ የሂሳብ ገቢና ወጪ ከመጀመሪያው ገንዝብ ያዥ ወቅት ጀምሮ እስካሁኑ እስከ 2014 ድረስ ነፃ በሆኑ ኦዲተሮች ተመርምሮ ለህዝብ እንዳልቀረበ ነው፡፡አይ ተደርጉኣል ከተባለም በተጨባጭ ፌዴሬሽኑ ሪፖርቱን ለህዝብ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡አቶ ብርሃኑ ገንዘቡ ባንክ ተከፍቶ እንዲቀመጥ ተጠይቆ ገንዝብ ያዥ በነበረበት ወቅት አሻፈረኝ እንዳለ እንደሚታወቅ ነው፡፡ባሁኑ ወቅትስ የፌዴሬሽኑ የባንክ አካውንት ተከፍቶ ገንዘቡ በባንክ ደረጃ የሚንቀሳቀስ ለመሆኑ ምንም ፍንጭ አይታይም፡፡በዚህ ላይ ፌዴሬሽኑ ማብራሪያ ሊሰጥ ይገበዋል፡፡

መኪናየማቆሚያቦታ

መኪናዎችን ከተፈቀደው ቦታ ሳይሆን ባልተፈቀደ ቦታዎች ሃላፊው እየነገራቸው በትእቢት በማቆማቸው ፖሊሶች መጥተው መኪናዎቹን በማስነሳታችው እያንዳንዱ ባለመኪን በትንሹ €300 ያህል እንደሚከፍል ነው፡፡ የፌዴሬሽኑ ተወካይ በማይክራፎን ደጋግም ቢናገርም ብዙ ስዎች በራሳችው ጥፋት ተቀጥተዋል፡፡ አንዳንዶቹም ሽጋ ኮረዳዎችን ለማንሆልል ትላልቅ ሽንጣም  መኪናዎች ተከራይተው ለማሳየት የመጡም  ከተቀጢዎቹ መሃከል እንደነበሩ ነው፡፡ 

ስለዓርብየመዝናኛምሽት

ዓርብ እለት ማታ የስፖርቱ ዝግጅት አካባቢ ባለው ከተማ ለምዩኒክ ቡድን እርዳታ የሚሆን የሙዚቃ ምሸት፤ በሲዲ ሙዚቃ  አጨዋቾች ውድድርና በታወቁት በይሁኔና በናቲ ዘፋኝነት ተዘጋጅቶ ለተሳታፊዎቹ በቂ በሆነ አዳራሽ ውስጥ የሙዚቃ አፍቃሪዎች በጣም በዝግጅቱ እንደረኩና ለአዘጋጆቹ ምስጋናውን እንዳቀረበ ነው፡፡ ለዚህ ምሽት መግቢያው €20 ነበር፡፡ይህ ዓይነቱ አዘጋጁና የሙዚቃ አፍቃሪዎች ረክተው የሚጠናቀቅ ዝግጅት ይደግም የሚያስኝ ነው፡፡

የቅዳሜው የሜዳ ላይዝግጅት

ቅዳሜ እስክ ቀኑ 6 ሰዓት ወይም ግማሽ ቀን ድረስ በጣም ሙቀት ነበር በሜዳ 1 ላይ ትሪቡን ላይ ከፌዴሬሽኑ ኢንፎርሜሽንስ ከሚተላለፍለት አጠገብ በግራ በኩል ትልቅ ዣንጥላ ተተክሎ ከተሪቩኑ ከፍተኛ ቦታ ላይ አንድ አግዳሚ ወንበር ላይ ከተለያዩ ከተሞች የመጡ አናቶች መቀመጫውንና ጥላው ሰር በመጠለል ፀሃይን ለመሽሽ አመቺ ቦታይዘው ተቀምጠዋል፡፡ልጆቻቸው ደግሞ በሜዳ ቁጥር 1 ላይ የኩኣስ መጫወት ፍላጎታቸውን ሲያረኩ በመመልከት ይወያያሉ፡፡በመጨረሻም አግዳሚ ወንበሩ በአንድ ክፉ ጀርመን ተነስቶባቸው የትሪቡኑ ስሚንቶ ላይ ጋዜጣ አንጥፈው መቀመጥ ተገደዱ፡፡የመጀመሪያውን የታዳጊ ወጣቶች የዋንጫ ጨዋታ እንደ ስፖንጅ ባይደላቸውም ከፀሃዩ ንዳድ ግን ራሳችውን በማዳን በጥላው ሰር ሆነው ለማየት ችለዋል፡፡ ልክ የሁለተኛው የህፃናት ጨዋታ ከተጀመረ በሁኣላ ሃይለኛ ዝናብ ከመብረቅ ነጎድጉኣድ ጋር ቢያንስ ለሁለት ሰዓት በመጣሉ፤ መጠለያ ፍለጋ ዱብዱብ ወደ አቅጣጫው ሆኖ ነበር፡፡ነጎድጉኣድ ያስከተለው ሃይለኛ ዝናብ ረገብ ብሎ በመጠኑ እየዘነበ በነበረበት ወቀት ሶስት ጨዋታዎች በቁጥር 1 ሜዳ ላይ ተካሂደዋል፡፡በመጨረሻም የሽልማት ሰነ ስርዓት ተካሂዶ በሜዳ ላይ የተዘጋጀው በዓል ፍፃሜ ሆኗል፡፡

የፌዴሬሽኑተወካዮችናየክለቦችተወካዮችስብሰባ

የፌዴሬሽኑ ተወካዮችና የክለቦች ተወካዮች ስብሰባም ተደርጉኣል፡፡የሚቀጥለው አዛጋጅም በዚሁ ስብሰባ ላይ ይወሰናል፡፡ በወሬ ደረጃ ሽኩሹክታ የሰማነው ኢትዮ  አዲስ ፍራንክፈርት እንደሆነ ነው፡፡ይህን ወሬ ሹክ ያለን ሰው በዚያው ቀጥሎ እንዴት ነው ፍራንክፈርት ብዙ ግዜ የማዘጋጅት እድል የሚሰጠው? ሲል አጉረምርሟል፡፡

የቅዳሜማታየሙዚቃምሽት

በቅዳሜው ምሽት ታዋቂው ድምፃዊ መሃሙድ አህመድ ከጃኖ ባንድ ጋርና በዓርብ ምሸት በሲዲ ሙዚቃ በማጫወት ውድድር አሸናፊ ከሆነው ጋር የሙዚቃ አፍቃሪውን ለማስደሰት እንደተዘጋጁ ነው፡፡መግቢያው €40 ሲሆን ዋጋው ቅዳሜ ከቀኑ 6 ስዓት ድረስ ትኬቱ በሜዳው አካባቢ መሽጥ እስከተጀመረበት ድረስ አይታወቅም ነበር፡፡ይህም እጅ ላይ የሚታስረው እልቁኣል ስለተባለ ውጭ ያሉ ሰዎች ሰብረው እንደገቡና በሁኣላም ሶስት መኪና ሙሉ ፖሊሶች መጥተው በስነ ስርዓት ተሰልፈው ከፍለው እንደገቡና ሙዚቃው እንደቀጠለ ነው፡፡ በመጨረሻም ጥሩና አዎንታዊ የሆኑትን አዳብሮ እንዲቀጥልና ጎጂና አሉታዊ የሆኑትን ደግሞ እንዲያስወግድ ለሚቀጥለው አዘጋጅ አገር ለማስተላልፍና በሚቀጥለው ዓመት የተሻለ ዝግጅት እንዲሆን በማስብ እስከዚያው በሰላም ሁላችንንም ያድረሰን፡፡   ከተንሳይት በቃና ኦገስት 4 ቀን 2014 ዓ.ም   Email:  tsedal2009@gmx.de

የአማራ ክልል አመራሮች ከግንቦት7 የኦህዴድ ደግሞ ከኦነግ ጋር እያበሩ ነው ሲል አቶ አዲሱ ለገሰ ያዘጋጁትና ለጠ/ሚ አማካሪዎች የተላከው ሰነድ አመለከተ

0
0

ነሃሴ ፩(አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰነዱ ላይ ኢህአዴግ የአመራር ችግር እንዳጋጠመው፣ የትራንስፎርሜሽኑ እቅድ አለመሳካቱ እንዲሁም በጋምቤላ ተማኝ መሪ መጥፋቱ ተዝርዝሯል።
በሃምሌ ወር መጨረሻ የተዘጋጀው ሰነድ ግልባጭ ለጠ/ሚኒስትሩ አማካሪዎች ለአቶ በረከት ስምኦን፣ ለአቶ ደስታውና ለአቶ ኩማ ደመቅሳ ተደርጓል።

የቀድሞው ም/ል ጠቅላይ ሚኒስትርና የኢህአዴግ የፖሊሲ ስልጠና ክፍል ሃላፊ የሆኑት አቶ አዲሱ ለገሰ ” የኢህአዴግን ተቃዋሚ ሃይላት ማንኮላሻ አቅም ግንባታ እና የአመራር ግንባታና የትራንስፎርሜሽን ጉዞ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ የፖሊሲ አማካሪዎች የቀረበ የሚለው ባለ 39 ገጽ ጽሁፍ፣ ኢህአዴግ ከላይ እስከታች የአመራር ችግር እንደገጠመው በዝርዝር ያቀርባል።

ጽሁፉ በመግቢያው “አገራችንን በፈጣን ቀጣይነት ያለውና ህዝቡ በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበት የእድገት ጉዞ ከድህነት አላቆ በተራዘመ ሂደት ከበለጸጉት አገሮች ጎራ ለማሰለፍ ይህንን ለማድረግ
የሚያስችል አላማ፣ ስትራቴጂ ስልቶችና ፖሊሲዎችን መቀየስ ይጠይቃል። በሌላ አነጋገር አቅጣጫውን በትክክል የሚያመላክት መስመር መቀየስ የትራንሰፎርሜሽን ስኬት የመጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ነው።
መስመሩን ለመቀየስ ይህንኑ ማድረግ የሚችል ብቃት ያለው አመራር ይጠይቃል። ኢህአዴግ በዚህ ፈተና ውስጥ ነው።” ብሎአል።

ሰነዱ ” ለአብነትም እነ አቶ መላኩ ፈንታን ማንሳት ይበቃል” ይልና ” ይህን ተከትሎ በአገሪቱ ያሉ አመራሮች ለመቀበል አለመቻላቸው እና የኡመድ ኡቦንግ ሃገር መክዳት፣ በጋምቤላ ክልል ያለው አመራር ታማኝና አስተማማኝ አለመሆኑ፣ የአማራ ክልል አመራሮች ከግንቦት ሰባት ጋር የተያያዘ አመራር መገኘት፣ የኦህዴድ አመራር ከኦነግ ጋር በማበር እና በአማራ ላይ የደረሰውን በደል በቸልታ መመልከት” በማለት ይጠቅስና “በአሁኑ ሰአት በትግራይ ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ( የአመራሩ ቸልተኝነት እንደተጠበቀ ሆኖ)፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በሃረሬ ምርጫውን ማሸነፍ የሚችል አመራር ድምጽ የማግኘት እድል አለው” ብአሎል።

ሰነዱ “የትራንስፎርሜሽን ትግል በውል ይጀመራል እንጅ አይጠናቀቅም ቢባልም በስጋት በተቀመጡት ክልሎች አሁንም አፋጣኝ ስራ ካልተሰራ ኪሳራ ሊያመጡ ይችላሉ” ብሎአል። የአመራሩ ደካማነት የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ሳይሳካ እንዲቀር አድርጎታል የሚለው ሰነዱ፣ ድርጅቱ ሰዎችን የሚመለምልበትና የሚያሰለጥንበት መንገድም ብዙ ችግሮች ያሉበት በመሆኑ፣ የምልመላ ዘዴውንና የስልጠና መንገዱን
እንዲቀይር ይመክራል።

ኢህአዴግን በመሰረቱ አራቱ ድርጅቶች መካከል ያለው ትውውቅ ደካማ በመሆኑ ከከፍተኛ እስከ መካከለኛ አመራር ያሉት በአንድ ማእከል ስልጠና እንዲሰጣቸው እየተደረገ መሆኑንም ተጠቅሷል። ኢህአዴግ እጅግ በጣም የሚበዛው አባሉ አርሶ አደር በመሆኑ ፣ የፖለቲካ መሪዎችን በብዛት ለመፍጠር አለመቻሉን የሚጠቅሰው ሰነዱ፣ ከእንግዲህ በዩኒቨርስቲዎችና በከተሞች ላይ ትኩረት ተደርጎ ሰዎችንየመፈለጉ ስራ እንዲጀመር ያሳስባል።

news

Health: የማህፀን በር ካንሰር

0
0

በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 65 ላይ ታትሞ የወጣ

የሴት ማህፀን ከስነ ተዋልዶ አካሎች ውስጥ አንዱ ሲሆን የተለያዩ ክፍሎችን የያዘና በፊት ለፊት በኩል ከሽንት ፊኛ በስተኋላ በኩል ደግሞ በትልቁ አንጀት የመጨረሻው ክፍል የሚወሰን አካል ነው፡፡ የሴት ማህፀንን ስንመለከት በመሰረቱ በሁለት ተከፍሎ እናየዋለን፡፡
- ዋናው የማህፀን አካል (Body of The Uterus)
- የማህፀን በር (Cervix)
Cervical Cancer
ይህ ዋናው የማህፀን አካል ሴት ልጅ ወላድ በሆነችበት የዕድሜ ክልል ውስጥ ከማህፀን በር ጋር ሲነፃጸር ሁለት እጥፍ ርዝመት አለው፡፡ የማህፀን በርም ዋናው የማህፀንን ክፍል ከውጪኛው ስነ ተዋልዶ ክፍል ጋር የሚያገናኝ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ መሰረታዊ ተግባራት አሉት፡፡
- በግብረ ስጋ ግንኙነት ጊዜ የወንድ ዘር ወደ ማህፀን እንዲገባ መንገድ ይከፍታል
- የወር አበባ የሚወጣበት መስመር ነው
- በእርግዝና ጊዜ ልጅ ከማህጸን አካል የሚወጣበት መንገድ ነው

በመሰረቱ ይህ የማህፀን በር ከነ አካቴው የተዘጋ ሲሆን በእነዚህ በሶስቱ ሁኔታዎች ክፍት ሆኖ ይገኛል፡፡ ይሄንንም ተንትነን ስንመለከተው፤

- በእንቁላል መመረት(Ovulation)ወቅት፡- የሴት ዕንቁላል ከእንቁላል ማቀፊያው ወጥቶ ወደ ማህፀን ቱቦ በሚጓዝበት ወቅት፣ ይህም የሚሆነው በየ28 ቀን ዑደት ባላት ሴት በ14ኛው ቀን ሲሆን ይህም የግብረ ስጋ ግንኙነት ይኖር እንደሆነ ለእርግዝና ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ነው፡፡
- በወር አበባ ወቅት፡- የወር አበባ ከማህፀን በሚወጣበት ጊዜ እንደየአስፈላጊነቱ ከ3-7 ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡
- ምጥ በሚጀምርበት ወቅት፡- የማህፀን አካል እየተኮማተረ ቀስ በቀስ የማህፀን በር ይከፈታል፣ ይህም የፅንሱን ጭንቅላትና አንዳንድ ጊዜም የፅንሱን መቀመጫ ሊያሳልፍ በሚችል መልኩ አጠቃላይ ክፍት ይሆንና ከወሊድ በኋላ ተመልሶ ቀስ በቀስ ወደ ቀድሞው ቦታ ይመለሳል፡፡
ስለ ማህፀን በር ጠቅላላ ግንዛቤ ይሄንን ያህል ከተመለከትን በብዛት ሴቶች የሚጠቁበትንና ከሴቶች የስነ ተዋልዶ አካላት ውስጥ በሁለተኛ ደረጃ በብዛት የሚይዘውን የማህፀን በር ካንሰር እንዳስሳለን፡፡ ይህ የማህፀን በር ካንሰር በብዛት የሚታየው ከ35-55 የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሴቶች ላይ ቢሆንም ማንኛውም የግብረ ስጋ ግንኙነት የጀመረችን ሴት ሊያጠቃ የሚችል ህመም ነው፡፡ ከግብረ ስጋ ግንኙነትም ጋር በብዛት ሊዛመድ የቻለበት ዋናው ምክንያት ሂውማን ፓፒሎማ ቫይረስ የተባለው በግብረ ስጋ ግንኙነት ጊዜ የሚተላለፈው የቫይረስ አይነት ለዚህ ችግር ዋናው መንስኤ በመሆኑ ነው፡፡ በማህፀን በር ካንሰር የመጠቃት ሁኔታ ከላይ እንደተጠቀሰው በብዛት የሚታይ ሁኔታ ቢሆንም ለዚህ ሁኔታ ያጋልጣሉ ተብለው የሚታመኑ በርካታ ሁኔታዎች አሉ፡፡
- በአነስተኛ ዕድሜ የግብረ ስጋ ግንኙነት መጀመር ዕድሜ ባነሰ ቁጥር የማህፀን በር በካንሰር የመጠቃት እድሉም አብሮ እየጨመረ ይሄዳል፡፡
- የግብረ ስጋ ግንኙነት አጋሮች ቁጥር በጨመረ ቁጥር
- የሰውነትን የመከላከያ ብቃት የሚቀንሱ የተለያዩ ሁኔታዎች በሚኖሩበት ወቅት
- በአባላዘር በሽታ መጠቃት እንዲሁም የኤች.አይ፣ቪ ቫይረስ በሰውነት ውስጥ መኖር
- የእርግዝና ቁጥር በጨመረ ቁጥር
- የወሊድ መቆጣጠሪያ መድሃኒት ለረጅም ጊዜ መውሰድ
- እንዲሁም ሲጋራ ማጨስ በጥቂቱ ይጠቀሳሉ፡፡
ይህ የማህፀን በር ካንሰርን እንደማንኛውም የካንሰር አይነት አደገኛ የሚያሰኘው አጀማመሩ ከዛው ከቦታው ይሁን እንጂ ጊዜ እያገኘ በመጣ ቁትር ወደ አካባቢው ወዳለ የማህፀን፣ የፊኛና፣ የአንጀት ክፍሎች ብሎም ወደ ተለያዩ የሰውነት ክፍሎች በመሰራጨት አንደኛ ደረጃ ሊያደርስ በመቻሉ ነው፡፡

የማህፀን በር ካንሰር በሚኖርበት ወቅት ሊታዩ የሚችሉ ስሜቶች

የማህፀን በር ካንሰር በሚኖርበት ወቅት በተለይ በሽታው በጀመረበት ጊዜያት ውስጥ ምንም አይነት ምልክት ላይታይ እንዲሁም የህመም ስሜት ላይሰማ ቢችልም ሁኔታዎች በቀጠሉ ቁጥር የሚታዩ ስሜቶች፤
- የወር አበባ በማይጠበቅበት ወቅት ከማህፀን ደም የመፍሰስ ሁኔታ በብዛት የሚታይ ስሜት ነው፡፡ ይህንንም ስንል ወትሮ ከሚታየው የማህፀን ፈሳሽ ጋር ደም የተቀላቀለ ፈሳሽ ማየት በውስጥ ሱሪ ላይ ትንሽ/ብዛት ያለው ደም ማየት፣ ማህፀንን በሚታጠቡበት ጊዜ ደም ማስተዋል፣ ከግብረ ስጋ ግንኙነት በኋላ ደም የመፍሰስ ሁኔታ ሊታይ ይችላል፡፡
- ወትሮው የሚታየው የማህፀን ፈሳሽ ብዛት መጨመር፣ ቀለሙን መቀየር እንዲሁም መጥፎ ሽታ መከተል ሊታይ ይችላል፡፡
- ሁኔታዎች እየተባባሱ በሄዱ ቁጥር በማህፀን አካባቢ ህመም መሰማት፡፡ ይህም በአብዛኛው በአንድ ወገን ብቻ የሆነ የህመም ስሜት ሆንና ወደ ወገብና ወደ እግር የመሰራጨት ባህሪ ይኖረዋል፡፡
- እንዲሁም ውሃ ሽንትና አይነ ምድርን መቆጣጠር የማይቻልበት ሁኔታ እንዲሁም በማህፀን በኩል አይነ ምድር ማየት ፊስቱላ መፈጠሩንና ሁኔታው መባባሱን ሊያመላክት ይችላል፡፡
- አጠቃላይ የሰውነት ድካም ስሜት፣ የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ የሰውነት ክብደት እጅግ በጣም መቀነስ እንዲሁም ደም ማነስ በብዛት የሚታዩ ሁኔታዎች ናቸው፡፡

የማህፀን በር ካንሰርን ለመከላከል አልያም በጊዜ ለማወቅ የሚረዱን መፍትሄዎች

የማህፀን በር ካንሰር ቀስ እያለና ጊዜውን እየወሰደ የሚባባስ ችግር እንደመሆኑ መጠን አንድ ሰው ምንም አይነት ስሜት የለውም ማለት ጨርሶ ምንም አይነት አደጋ ላይ አይደለም ማለት አይደለም፡፡ ለዚህም ከዚህ በታች ሁኔታውን ለመከላከል ወይም በጊዜ ለማወቅ የሚረዱንን መንገዶች እንመለከታለን፡፡

- ከላይ የተጠቀሱትን ለማህፀን በር ካንሰር ያጋልጣሉ የተባሉትን ነጥቦች ከግንዛቤ በማስገባት አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ
- በአሁኑ ወቅት ባደጉ ሀገሮች ውስጥ የማህፀን በር ካንሰር መንስኤ የሆነውን ቫይረስ የሚከላከል ክትባት በዓለማችን ዝግጁ ሆኖ ቢገኝም ይህ ክትባት ባደጉ ሀገሮች ውስጥ ብቻ በመገኘቱና እንዲሁም ዋጋው ከፍተኛ እንደመሆኑ ሀገራችን ላለው ሁኔታ እንደ መከላከያ ዘዴ ልንጠቅሰው አንችልም፡፡
- ማንኛውም ዕድሜው ከ18-40 ዓመት የሆናት ሴት ቢያንስ በየ3 ዓመቱ የማህፀን ሐኪም ጋር በመሄድ አጠቃላይ የማህፀን ምርመራ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡
- ማንኛውም ከ18-65 የዕድሜ ክልል ውስጥ ያለች ሴት ወይም የግብረ ስጋ ግንኙነት ከ18 ዓመቷ በፊት የጀመረች ሴት ለመጀመሪያው 3 ዓመታት በየዓመቱ የሚደረግ የፖፕ ስሚር ምርመራ ማድረግ፣ ለሶስት ተከታታይ ዓመታትም ምንም አይነት ምልክት ያልታየ እንደሆነ ከዛ በኋላ በየ3 ዓመቱ ይህንን ምርመራ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡ አብዛኛው ከ65 ዓመት በላይ የሆኑ ሴቶች ላይ ይህ ምርመራ ወሳኝነቱ እየቀነሰ ይሄዳል፡፡
ከላይ እንደተጠቀሰው ይህ የማህፀን በር ካንሰር ምንም አይነት ስሜት ላይኖረው እንደመቻሉ መጠን በየ1-3 ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ የፓናስሚር የተባለው ምርመራ ከመጣ በኋላ የማህፀን በር ካንሰር ሳቢያ የሚከተለውን የሞት ቁጥር 50 በመቶ ቀንሶ እናየዋለን፡፡
ይህ ምርመራ በመሰረቱ ትንሽ እንጨትና እንዲሁም አነስተኛ ብሩሽ በመተቀም ከማህፀን በር ላይ ናሙና የሚወስድበት የምርመራ አይነት ሲሆን በምርመራው ወቅት ህመም አለ እንኳን ብንል በጣም አነስተኛ የህመም ስሜት የሚያስከትል የምርመራ አይነት ነው፡፡ ይህ ከማህፀን በር የተወሰደው ናሙና በማይክሮስኮፕ ከተመረመረ በኋላ አንዳች አይነት ጥርጣሬን የሚያስከትል ሁኔታ የተፈጠረ እንደሆነ በትንሽ መሳሪያ ተጠቅሞ እንደየአስፈላጊነቱ የታየ ናሙና ወስዶ በደንብ ማጤን ተገቢ ነው፡፡
በአብዛኛው ሴቶች ፓፕስሚር ምርመራ ከማድረጋቸው በፊት ለ24 ሰዓታት ማህፀናቸው ባይታጠቡ እንዲሁም በማህፀን የሚገባ ምንም አይነት መድሃኒት ባይጠቀሙ ይመረጣል፡፡

ይህ ችግር በሚከሰትበት ወቅት ምን ማድረግ ተገቢ ነው?
አንድ ሴት የማህፀን በር ካንሰር አላት ካልን የሚቀጥለው እርምጃ የሚሆነው የካንሰሩ ደረጃ ምን ላይ ነው የሚለውን ማወቅ ይሆናል፡፡ ይሄም የተለያዩ ምርመራዎችን በማድረግ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ በመቀጠል ሐኪምዎን አማክረው እንደየአስፈላጊነቱና እንደየደረጃው ተገቢውን መፍትሄ ማግኘት ያስፈልጋል፡፡
ለዚህም ከላይ እንደተጠቀሰው በየጊዜውና እንደየአስፈላጊነቱ ምርመራ ማድረግ ከዚህም በተጨማሪ ደግሞ ማንኛውም አይነት ከላይ የተጠቀሱት ሁኔታዎችና ስሜቶች በሚከሰትበት ወቅት በቶሎ የህክምና ባለሙያ ማማከር ግድ ይላል፡፡ ለዚህም ሴቶች ሁሌ ለጤናችን ትኩረት እናድርግ እላለሁ፡፡

መኢአድና አንድነት ውህደታቸውን ለማራዘም መገደዳቸውን ገለፁ

0
0

ለውህደቱ መራዘም  ምርጫ ቦርድን ተጠያቂ አድርገዋል 
መንግስት በግል ሚዲያዎች ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አውግዘዋል

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ነገ ሊያካሂዱት የነበረውን ውህደት ለማራዘም መገደዳቸውን አስታወቁ፡፡ ለውህደቱ መራዘም ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ተጠያቂ አድርገዋል፡፡ 

udJ&AEUPበሌላ በኩል  መንግስት በግል ሚዲያዎች ላይ እየወሰደ ያለው እርምጃ፣ የህዝብን መረጃ የማግኘት መብት የሚገድብና የመናገር ነፃነትን የሚያሳጣ በመሆኑ እንደሚያወግዙት ፓርቲዎቹ ገልፀዋል፡፡ 
“መኢአድና አንድነት ወደ ሰላማዊ የትግል ጦርነት ውስጥ መግባታቸውን ለህዝብ ማሳወቅ ይወዳሉ” በሚል ርዕስ ከትላንት በስቲያ ፓርቲዎቹ  በሰጡት መግለጫ፤ “መኢአድ በ2005 ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ምዕላተ ጉባኤ ያልተሟላ በመሆኑ መዋሀድ አትችሉም የሚል ተልካሻ ምክንያት በማቅረብ ምርጫ ቦርድ  ውህደቱን እንድናራዝም አስገድዶናል  ብለዋል፡፡ 
በ2005 በተካሄደው ጉባኤ ከ600 የጠቅላላ ጉባኤ አባላት 390 ያህሉ ተገኝተው ህጉ በሚፈቅደው መልኩ ጉባኤው መካሄዱን ራሱ ምርጫ ቦርድም ያውቃል ያሉት የመኢአድ ሃላፊዎች፤ጉባኤው ሲካሄድ የምርጫ ቦርድ ተወካዮች መጥተው ምዕላተ ጉባኤው መሙላቱን ቢያረጋግጡም ቦርዱ ግን ምዕላተ ጉባኤው አልተሟላም በሚል ለአንድ ዓመት ያህል አዎንታዊ ምላሽ ሳይሰጥ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ 

“በህወሓት /ኢህአዴግ የሚመራው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ፣ በሰላማዊ ትግሉ ላይ ከፍተኛ መሰናክሎችን በመፍጠር ከዚህ ቀደም የተደረጉ አገር አቀፍ ምርጫዎችን በማዘረፍ ህዝብ የድል ባለቤት እንዳይሆን አድርጓል” ያሉት ፓርቲዎቹ፤ አሁን ደግሞ ጠንካራ ፓርቲዎች ተዋህደው በተደራጀ ሃይል በሰላማዊ ትግሉ እንዳይገፉ አሳማኝ ያልሆነ ምክንያት በመደርደር ውህደታችንን እንዳንፈጽም የሚያደርገውን ጫና እንቃወማለን ብለዋል።

“ምርጫ ቦርድ እንቅፋት ቢፈጥርም ፓርቲዎቹ ግን በሃሳብና በቁርጠኝነት ተዋህደዋል” ያሉት የአንድነትና መኢአድ አመራሮች፤በተጠናከረ ሃይል በሰላማዊ ትግሉ በመግፋት አላማቸውን እንደሚያሳኩ ገልፀዋል፡፡ 

የምርጫ ቦርድን ውሳኔ አስመልክቶ አስተያየታቸውን የጠየቅናቸው የአንድነት ፕሬዚዳንት ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው፤ በዚህ ጉዳይ ምርጫ ቦርድ ሄደው እንደነበር አስታውሰው መኢአድ በወቅቱ ለምርጫ ቦርድ የላከው የምዕላተ ጉባኤ ዝርዝር 285 እንደነበርና ኮረሙ ተሟላ የሚባለው ከ300 አባላት በላይ በስብሰባው ሲሳተፉ እንደሆነ  ከምርጫ ቦርድ እንደተገለፀላቸው ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ 

መኢአድም የስም ዝርዝር ወረቀቶች ተረስተው መቅረታቸውን በመጠቆም  ለምርጫ ቦርድ 118 ተጨማሪ የተሳታፊ አባላትን ዝርዝር ቢያቀርብም  በወቅቱ ያልተላከ የአባላት ስም ተቀባይነትና ተአማኒነት የለውም በሚል የቦርዱ የህግ ክፍል አለመቀበሉን የገለፁት ኢ/ር ግዛቸው፤“መኢአድ ህጋዊና አገር አቀፍ ፓርቲ ሆኖ ሳለ በማህተምና በፊርማ የተረጋገጠ ማስረጃ ሲያቀርብ እንዴት አይታመንም ትላላችሁ፤አይታመንም የምትሉበትን ምክንያት በማስረጃና በመረጃ አቅርቡ” በማለት ቢከራከሩም ከቦርዱ ምላሽ  አለማግኘታቸውን ጠቁመዋል፡፡  
“ኮረም ሞላ አልሞላ የሚለው ለውህደቱ እንቅፋትነቱ አላሳመነኝም” ያሉት የአንድነት ፕሬዚዳንት፤ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ጉባኤ ሲካሄድ የራሱን ታዛቢዎች በማስቀመጥ ታዛቢዎቹ ለቦርዱ ሪፖርት እንደሚያቀርቡ ጠቁመው፣ቦርዱ ታዛቢዎች ያቀረቡለትን ሪፖርት ከፓርቲው ሪፖርት ጋር በማመሳከር ችግሩን መፍታት ይችል ነበር ብለዋል፡፡ “መኢአድ ጉዳዩን በአፋጣኝ ወደ ፍ/ቤት መውሰድና መብቱን በህግ ማስከበር አለበት” ሲሉም ኢንጂነር ግዛቸው አሳስበዋል፡፡ 

በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የጽ/ቤቱ ምክትል ዋና ሃላፊ አቶ ወንድሙ ጐላ ስለጉዳዩ ጠይቀናቸው ሲመልሱ፤ምርጫ ቦርድ ፓርቲዎች የመሃድ መብት እንዳላቸውና መዋሃዳቸው የተሻለ እንደሚሆን እንደሚያምን ጠቁመው ነገር ግን ፓርቲዎቹ በምርጫ ቦርድ እንዲያሟሉ የሚጠየቁትን መስፈርት ማሟላት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ “በአሁኑ ወቅት እንዲያሟሉ የጠየቅናቸውን መስፈርቶች በደብዳቤ ገልፀናል” ያሉት ሃላፊው፤እነዚህን ነገሮች እስካሟሉ ድረስ መዋሃድ የማይችሉበት ምክንያት እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ ፓርቲዎቹ እንዲያሟሉ የተጠየቁትን መስፈርቶች አስመልክቶ የጠየቅናቸው ሃላፊው፤ “አሁን ሩቅ ቦታ ነኝ፣ በእጄ ላይ ዝርዝሮቹ የሉም፣ ሆኖም ያላሟሉት ነገር እንዳለ ግን ግልጽ ነው” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ 
በሌላ በኩል መኢአድና አንድነት፤መንግስት በግል ሚዲያዎች ላይ እየወሰደ ያለው እርምጃ የህዝብን መረጃ የማግኘት መብት የሚገድብና የመናገር ነፃነትን የሚያሳጣ በመሆኑ እንደሚያወግዙት አስታውቀዋል፡፡ ሰሞኑን የፍትህ ሚኒስቴር በአቴቪ ባሰራጨው መግለጫ፤ ህገመንግስቱን በሃይል ለመናድና የሃይማኖት አክራሪነትን በመስበክ አመፅ ቀስቅሰዋል ባላቸው አምስት ተጠርጣሪ የግል ፕሬሶች  ላይ  ክስ መመስረቱን ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ 

ምንጭ፥ –  አዲስ አድማስ

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live