አምባቸው ደጀኔ በኔ ላይም ከታወጀው ትልቅ ጦርነት ልጀምር፡፡ በኔና በመሰሎቼ ላይ ከተከፈቱብን ጦርነቶች አንዱና ሕይወት ቀጣፊው በብስጭት ምክንያት የሚከሰቱ ህመሞች ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት ብዙ ሰው እየቀወሰና ጨርቁን ጥሎ እያበደ ነው፡፡ ሰካራም በዝቷል፤ ጎዳና ተዳዳሪ በዝቷል፡፡ ከለዬለት ዕብደት በመለስ በደም ግፊትና ስኳርን በመሰሉ ተዛማጅ በሽታዎች የምንሰቃይ በዝተናል፤ ኦሮሙማ በዚህም የጦር ግምባር ድል በድል እየሆነ ነው፡፡ አማራንና አማራ ነክ የሆነን በሙሉ ማውደም፡፡ የምታውቁትን ስዘረዝር አልገኝም፡፡ ለኔ አዲስ የሆነ አሁን የሰማሁትን ግን ልጠቀስ፡፡ እሱም በሰሜን ሸዋው ሰሞነኛ የኦሮሙማ ወረራ የአማራ ገበሬዎችን ከነቤተሰባቸው ከመግደል ጎን ለጎን የጎተራ እህል እየገለበጡና የሚዘረፍን ተንቀሳቃሽ ንብረት እየዘረፉ በአይሱዙ እንደሚጭኑ የተሰራጨው አሳዛኝ ዜና ነው፡፡ ወሰን የሌለው ዕብሪትና ጥጋብ፡፡ ብቻ
↧