የዐቢይ አሕመድ ቃል አቀባይ የሆነው የኦሮሙማው አስኳድ ታዬ ደንደአ እነሱ ሲያደርጉ የኖሩትን አማራውም የሚያደርግ እየመሰለው መላው አማራ በዐቢይ አሕመድ የታወጀበትን የጅምላ ፍጅትና የዘር ማጥፋት በመቃወም የሚያደርገውን የኅልውና ተጋድሎ ከግብጽና ሱዳን ጋር ለማገናኘት እየኳተነ ነው። ታዬ ደንደአ ራሱ እድሜ ዘመኑን የታገለለት ኦነግ ከስንቅ እስከ ትጥቅ ሲቀርብለት የኖረው የኢትዮጵያ ጠላቶች በሆኑት የግብጽና የሱዳን አገዛዞች ነው። በግብጽ ብሔራዊ ቴሌቭዥን በተላለፈውና ፕሬዝደንት ሙርሲ በመራው ጉባዔ ግብጽ በኢትዮጵያ ላይ ያላትን ፍላጎት ለማስፈጸምና ኢትዮጵያን ለማዳከም ይጠቅመኛል ያለችውም ኦሮሞን እንጂ አማራን አልነበረም። ግብጽ ታላቁን የአባይ ግድብ በቦንብ ታጋየው ዘንድ በአደባባይ የጠየቁም እነ ታዬ ደብደአ የአበባ እቅፍ ይዘው የተቀበሏቸው የኦሮሞ ብሔርተኞች እንጂ የአማራ ልጆች አይደሉም። ዛሬም ድረስ መቀመጫቸውን
↧