Pope Francis urges Egypt, Ethiopia, Sudan to continue talks over disputed dam
COVID-19 is crushing Ethiopian entertainers, just when we need them the most
Open Letter to Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia
Hiber Radio Daily News Aug 16, 2020
State Terrorism in Ethiopia
Hiber Radio Daily News Aug, 17 2020
The Dogs of Propaganda War Keep on Barking, the Ethiopian Camel Keeps on Walking…
ዘር-ፍጅት ወንጀለኞችን ለሕግ ለማቅረብ ትብብር ጥሪ
በሃገራችን ብሔርን መሠረት ያደረገ የፖለቲካ አገዛዝ ተግባራዊ ከሆነበት ከ1983 ዓም ጀምሮ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በ ብሔር ተለያይቶ እንዲፉጅ መንግሥት መርዘኛ ተንኮል ሲፈጸም ቆይቷል ። የኢትዮጵያን መዐከላዊ መንግሥት ላለፉት 27 አመታት ተቆጣጥሮ የቆየው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ሕወሃት) ሕዝባችን ለዘመናት ገንብቶት የኖረውን ሕብረ ብሄራዊ አንድነቱን በማላላትና እርስ በእርስ በጠላትነት እንዲተያይ በማድረግ ዛሬ ለደረስንበት አስከፊ ብሄራዊ ቀውስ ዳርጎናል ። ሕወሃት በዋናነት፣ ሌሎች ተገንጣይ ኃሃይሎች በተላላኪነት፣ በብዙ ሺህ ለሚቆጠሩ ሰላማዊ ዜጎች ሞት፣ መፈናቀልና ስደት ምክንያት ሆነዋል ። በተለይም የኦሮሞ ነጻነት ግንባር በአርባጉጉ፣ በወተርና በበደኖ ያካሄደው አንድን ብሔር መሠረት ያደረገ ዘግናኝ ጭፍጨፉ የሚዘነጋ አይደለም ። እነዚህ ጽንፈኞች የአማራን ተወላጆችና ክርስቲያኖችን በመነጠል ላደረሱት የጅምላ ጭፍጨፉ በተገቢው
The post ዘር-ፍጅት ወንጀለኞችን ለሕግ ለማቅረብ ትብብር ጥሪ appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
ማላጅ –ያሚ ፀጋ
ትናንት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ከፍተኛ የመንግስት እና የህዝብ ተጠሪዎችን በመጋበዝ በጅምር እና በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙትን የዕንጦጦ እና ሸገር መዝናኛ ስፍራወችን ( የልማት ስራወችን) የማስጎብኘት ፣ ማብራሪያ እና ትንተና መስጠታቸዉንና ይህ በሚመለከት ያላቸዉን ብሄራዊ ቀናኢነት እና ጥረት ልባዊ ተነሳሽነጽ በማድነቅ ሲሳይ መንግስቴ(ዶ/ር) በፅሁፍ ገልፀዋል፡፡ እኛ ኢትዮጵያዉያን የክቡር ጠቅላይ መኒስቴር አብይ አህመድ ምኞት እና ራዕይ ኢትዮጵያን ወደ ቀደመ የክብር ማማ ሠገነት ለማዉጣት እና ህዝቧን ከተረጅ እነት እና ጠባቂነት ባርነት ነጻ ለማድረግ እንደሆነ ከባዕለ ሲመት ንግግር(መግለጫ) አስከ አሁን ዕለት ብርቱ ድካም እና ተጋድሎ የሞት ሽረት ትግል ከሰፊዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ማድረጋቸዉ አይካድም፡፡ ነገር ግን ይህን ብሄራዊ እና ህዝባዊ ዕድገት፣ ልማት እና
The post ማላጅ – ያሚ ፀጋ appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
ተመስገን እንበል (ዘ-ጌርሣም)
ተመስገን ፈጣሪ ሌላ ምን ይባላል ሰው የሰጠው ቢሆን ዋጋ ያስከፍላል ከምስጋና በቀር የማትፈልግ ሌላ በአንድ ላይ ተንሰስተን እንግባ ምህላ እናመስግን አንተን ከፍ ከፍ አድርገን እንባችን ይታበስ ኢትዮጵያ ትወደስ ከፍ ብላ በልፅጋ በዓይናችን ልናይ ነው ችግሮች ሲጠፉ ትውልድ ደስ ሲለው ውጡ እናመስግነው ወገኖች በሙሉ የኢትዮጵያ ትንሣዔ ገሃድ ሁኗል አሉ የአባይ ግድብ አልቆ መሞላት ጀምሯል ምኞት የነበረው ይኸው በዓይን ታይቷል የጨለማው ዘመን ሊገፈፍ ተቃርቧል አኬሩን በእጃችን ቁጭ አድርጎልናል እወቁበት ይላል የመጣልን ዕድል ተግባብተን በመኖር እንድንሆን ድል በድል ደህና ሁን ጨለማ ደህና ሁን ፅልመት አባይ ሊያበራ ነው ከዓመት እስከ ዓመት እልል በል ወገኔ በአራቱም ማዕዘናት ደስታችን ታወጀ ተነገረ ብሥራት የተጫወተብን ያ ጨለማ ዘመን
The post ተመስገን እንበል (ዘ-ጌርሣም) appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
በአቶ ጃዋር መሐመድ ቤት በብርበራ የተገኘው የሳተላይት መሣሪያ ለግለሰብ የማይፈቀድና ሕገወጥ መሆኑ መረጋገጡ ተነገረ
ከድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዞ በተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ተጠርጥሮ በእስር ላይ በሚገኘው አቶ ጃዋር መሐመድ መኖሪያ ቤት የተገኘው የሳተላይት መሣሪያ በግለሰብ እጅ መያዝ የሌለበት ከመሆኑም በተጨማሪ ሕገወጥ መሆኑ እንደተረጋገጠ ዓቃቤ ሕግ ተናገረ፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ዳይሬክተር አቶ ፈቃዱ ፀጋ እንደገለጹት፣ የተጠርጣሪው ቤት ሦስት ጊዜያት ተበርብሯል፡፡ በዚህም የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስና የሳተላይት መሣሪያዎች መገኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ የሳተላይት መሣሪያው ከአምስት እስከ 25 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የኔትወርክ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑንና የአገሪቱ ቴሌኮም የኔትወርክ አገልግሎት ቢቋረጥም በራሱ የሚሠራ መሆኑን አቶ ፈቃዱ ገልጸዋል፡፡ ይሁን እንጂ ሳተላይቱ በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች እየተጻፈ እንደሚገለጸው የሁሉንም ስልክ መጥለፍ አይችልም፡፡ ነገር ግን በተጠቀሰው ርቀት ላይ
The post በአቶ ጃዋር መሐመድ ቤት በብርበራ የተገኘው የሳተላይት መሣሪያ ለግለሰብ የማይፈቀድና ሕገወጥ መሆኑ መረጋገጡ ተነገረ appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
ጠቅላይ ሚኒስተር ዶር. ዓቢይ:መስፍን ወልደ ማርያም
ጠቅላይ ሚኒስተር ዶር. ዓቢይ ለኢትዮጵያ የጀመርከው እቅድ ሰፊና ረጅም ነው፤ ጊዜ ያሰፈልግሃል፤ ረዳቶች ያስፈልጉሃል፤ ጉልበት ያስፈልግሃል፤ የሕዝብ ፍቅር ያስፈልግሃል፤ የማርያም ድጋፍ ያስፈልግሃል፤ እግዚአብሔር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሲል፤ ለአንተና ለቤተሰብህ ሲል፤ የብዙ ጠላቶችህን አቅም አዳክሞ የአንተን አቅም ያበርታልህ፤ ያሰብከውን ሁሉ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅምና ለአንተ ታሪከ የምታመቻችበት ዕድሜና ጤንነት ይስጥህ፡፡ መስፍን ወልደ ማርያም ነሐሴ 10/2012
The post ጠቅላይ ሚኒስተር ዶር. ዓቢይ:መስፍን ወልደ ማርያም appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
አብይ፣ ለማና የጃዋር ካልኩሌተር (አበበ ገላው)
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና ኦቦ ለማ መገርሳ በጣም የቅርብ ወዳጆች ነበሩ። ከወዳጅነትም ባለፈ እንዱ ለሌላው መከታ የነበረ ወንድማማቾች አንደነበሩ ይነገራል። በስፋት እንደምታወቀው ህወሃትን አሽምድምዶ በጣለው ፈታኝና አደገኛ ውስጣዊው የኢህዴግ ትግል ውስጥ የሁለቱ ሚና እጅግ ጉልህ ነበር። የዛሬ ሁለት አመት እድል ገጥሞኝ በዚህ በዋሽንግተን ዲሲ ወተርጌት ሆቴል ከሁለቱም ጋር ቁጭ ብዬ በተነጋገርኩበት አጋጣሚም የተረዳሁት ነገር ይሄንኑ ነበር። ህወሃትን የታገሉት ነፍሳቸውን አስይዘው አንድ አይናቸውን ገልጠውና “ጫማቸውን ሳያወልቁ” እየተኙ እንደነበር አጫውተውኛል። በእውነትም በመልክ ባይመሳሰሉም በጣም የሚከባበሩ መንትዮች ነበር የመሰሉኝ። ታዲያ በመሃላቸው ምን ሰይጣን ገብቶ ነው በዚህ ወሳኝ ሰአት ሊለያዩና በተቃራኒ መንገድ ሊጓዙ የወሰኑት? ለነገሩ ፖለቲካ ባህሪው ውስብስብ ነው። የፖለቲካ ስትራቴጂና ያመለካከት ልዩነት ሊኖር
The post አብይ፣ ለማና የጃዋር ካልኩሌተር (አበበ ገላው) appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
ዝምታ ወርቅ አይደለም –ከአባዊርቱ!
መግቢያ! የተከበሩ ልኡል ራስ መንገሻ ስዩም ለኢትዮጵያ ብዙ ውለታ የዋሉ ፣ ስመጥርና ምሁር የሆኑ የትግራይ ተወላጅ ፍፁም ኢትዬጵያዊ ናቸው። የ ሀያሰባቱ አመት ይቅርና ከሁለት አመት ለውጥ እድሜ በሁዋላ እንኳ በአንዳንድ ጉዳይ እንደምን እንዳስቻላቸው ግራ ይገባኛል። እነዚህ ፅልመቶች መቼስ ከማርስ አይደለም የፈለቁት ከትግራይ እንጅ። በትግራዋይ ስም ይህ ሁሉ ግፍ ሲፈፀም ትግራይ የኢትዮጵያችን አፅመእርስት እንዳልሆነች ነገር ሌላው ጥቅመኛና ባለጊዜ እንኳ ቢቀር የልኡልነታቸው አይነቱ የታሪክ ማህደር ዝምታ በበኩሌ እጅጉን አሳዝኖኛል። በተለይም ስለ መልካም ማንነታቸውም ስለማውቅ። እነ ህውሀት ወልቃይትን፣ የቤገምድርና ሰሜንን ግዛት በትግራይ ታሪክና በሳቸውና በአባታቸው እርስት የማይታወቁትን እየጠቀለሉና ከአማሮቹ ደም እያቃቡን እየሰሙ እንደምን አስቻላቸው ያሰኛል በውነቱ። ውድ ኢትዮጵያውያን/ውያት ወገኖች! አባቶቻችን ወረራን በደምና አጥንቶቻቸው
The post ዝምታ ወርቅ አይደለም – ከአባዊርቱ! appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
ዙፋኑ ላይ ተቀምጠው በትረ መንግሥቱን ያልጨበጡ መሪ –በገ/ክርስቶስ ዓባይ
በገ/ክርስቶስ ዓባይ ነሐሴ 10 ቀን 2012 ዓ/ም በዓለም ላይ አገር መሪ ለመሆን የማይመኝ ሰው የለም። ነገር ግን ለዚህ አስተሳሰብ ከልጅነታቸው ጀምረው ዝግጅት የሚያደርጉ ጥቂቶች ናቸው። ከእነዚህ ውስጥም ለዚህ ታላቅ ኃላፊነት የሚበቁት እጅግ በጣም ኢምንቶቹ ብቻ ናቸው። መሪ እንዲሆኑ ከልጅነታቸው ጀምሮ በወላጆቻቸው ተኮትኩተው ካደጉት ውስጥ ጥቂቶችን መግለጽ አስፈላጊ ይሆናል። በእኛው አገር ከምናውቃቸው ብንጀምር ለምሳሌ አፄ ኢዮአስን መጥቀስ ተገቢ ይመስለኛል። አፄ ኢዮአስ በሕፃንነታቸው ጀምሮ በወላጆቻቸው ለአገር መሪነት የታጩ ሰው ነበሩ። አፄ ኢዮአስ የአፄ በካፋ ልጅ ናቸው። ነገር ግን በወጣትነት ዕድሚያቸው እንዳሉ ከጋላ (አሁን ኦሮሞ) ተስፋፊ ማኅበረሰብ ጋር በተደረገ ጦርነት ተማረኩ። ከዚያም በተደረገ የጦር ምርኮኝነት ልውውጥ እርሳቸውም ተፈትተው ወደ አገራቸው ወደ ጎንደር ተመለሱ።
The post ዙፋኑ ላይ ተቀምጠው በትረ መንግሥቱን ያልጨበጡ መሪ – በገ/ክርስቶስ ዓባይ appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
“መከላከያ” (ለወላይታ ወገኖቼ)
እውን እንደ ስምህ፣ ቢሆንማ ግብርህ፣ አገርን ከጠላት፣ ወገንን ከጥቃት፣ መከላከል ነበር፤ የጀግንነት ስራ፣ ዘወትር ስምህን በክብር የሚያስጠራ፤ …መብት ጠያቂዎችን፣ ንጹሃን ዜጎችን፣ እጃቸውን አጣምረው፣ ባዶአቸውን ቆመው፣ አልሞ መረሸን… አረመኔ ተግባር የፈሪ ዱላ ነው!! እስኪ ልባም ከሆንክ፣ ለአገር አሳቢ፣ የትውልድን ጋሻ ወራሽ ተረካቢ፣ ከጨካኝ አርዮሶች፣ ከሰው ልጅ አራጆች፣ በዘር ሳትወግን ከከንቱ ከንቱዎች…፣ ንጹሃንን ታደግ፤ ሁናቸው ከለላ፣ ፊትህን አዙረህ፣ በ’አውሬ’ ሳታስበላ!! ጌታቸው አበራ ነሐሴ 2012 ዓ/ም (ኦገስት 2020) *በዘርና በቋንቋ የምትሸነሸን ኢትዮጵያ፣ ህልውናዋና መፃዒ ዕድሏ፣ እንደ ዜጋ የሚያሳስበኝና በግሌ ሃሳቡን የማልደግፍ ብሆንም፣ በአገሪቱ ህግ ቦይ ተቀዶለት ለሌሎች በተተገበረበት ሁኔታ፣ “ማን ከማን ያንሳል” ብለው የድርሻቸውን በሰላማዊ መንገድ ለመጠየቅ በተነሱ የወላይታ ወገኖቼ ላይ የተፈጸመውን አስነዋሪ
The post “መከላከያ” (ለወላይታ ወገኖቼ) appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
ሰውነት ውሀ ነው! –በላይነህ አባተ
ደም በስብከት አጥቦ ሟችን እሚረሳው፣ አቢይ ጉድጓድ ሲምስ ዝምሎ እሚከተለው፣ በጅ የማይጨበጥ ሰውነት ውሀ ነው፡፡ ሲክብ እንደ ደለል ሲያፈርስም እንደ ጎርፍ፣ ሰውነት ውሀ ነው ቦይ ሲያገኝ እሚፈስ፡፡ በስድስተኛው ቀን መለኮት ሲፈጥረው፣ ቀጥ ብሎ እንዲሄድ ከአፈር ቢያበጃጀው፣ ትዕዛዙን አፍርሶ እጥፍ ዘርጋ እሚለው፣ ቦይ ባየበት ፈሳሽ ሰውነት ውሀ ነው፡፡ የግሪኩ ጠቢብ ቴልስ እንዳስተማረው፣ የገላ ይዘቱ ሰውነት ውሀ ነው፡፡ የጦቢያ ሊቃውንት ጥንት እንደጠበቡት፣ ገላ የተሰራው ከውሀ አፈር እሳት፡፡ ሳይንስ በምርምር እንዳረጋገጠው፣ ሰባ በመቶውን ሰውነት ውሀ ነው፡፡ አስተዋይ ተመልካች እንደሚታዘበው፣ ስግብግቡን ገላ ሰውነት የሞላው፣ ቦይ ሲቀደድለት እሚፈስ ውሀ ነው፡፡ ቀና ብሎ ሲሄድ ጠጣር መስሎ ታይቶን፣ ሰው ፈሳሽ መሆኑን ደጋግመን ዘነጋን፡፡ ቀጥ ብሎ እሚቆም ግማዴ
The post ሰውነት ውሀ ነው! – በላይነህ አባተ appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
ጠ/ሚ አብይ አህመድ፣ “በተጨቆኑ ቀልዶች”በከንቱነት የተቀለደበትን ቤተመንግሥት የገነት ተምሳሌት አድርገውታል።…–መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ
–“አዲስ አበባ ፋሽን የለበሱ፣ብዙ ፖለቲካ የሚያወሩ፣መዓት ፊትአውራሪ መሸሻዎች አሉ።…” አዳም ረታ ኢትዮጵያ በ10 ክልላዊ መንግሥታት እና በሁለት የከተማ መሥተዳድሮች በፊደራል ሥም ቋንቋን መሠረት አድርጋ የአገዛዝ ወይም የአሥተዳደር ሥርዓት ከመዘርጋቷ በፊት ፤ ዛሬ በሸገር 107 ፖርቲዎች መሽገው፣ ለመጨረሻው የመንግሥት ሥልጣን እንፎካከራለን እያሉ ፣በጎሳ፣በነገድ፣በቋንቋ እና “በሥልጡን ፓርቲ” ሥም በየፊናቸው “ሀይ ሎጋ !” እያሉ አራት ኪሎ ቤተመንግሥት ለመግባት በብሔራዊው ምርጫ ቦርድ ከመመዝገባቸው በፊት ፤ የዛሬ 200 ዓመት በፊት አዲስ አበባ ፣በተለያየ ሥም ትጠራ ነበር። ፊኒፊኔ እና በረራ ይጠቀሳሉ።እርግጥ ፍል ውሃ አካባቢ ፍልውሃ እንደተባለ እና ከፍል ውሃው አፈነጣጠቅ የተነሳ የወጣ ሥም ነው።በረራ ደግሞ ግልቢያ ማለት ነው ።በዘመኑ ፍቺ።በረራ በእርግጠኝነት የአዲስ አበባ የቀድሞ ሥሞ ነው
The post ጠ/ሚ አብይ አህመድ፣ “በተጨቆኑ ቀልዶች” በከንቱነት የተቀለደበትን ቤተመንግሥት የገነት ተምሳሌት አድርገውታል።… – መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
ጥያቄ፦ ከእኛ ለእኛ –ጠገናው ጎሹ
የአገራችን ፖለቲካ በሸፍጥና በሴራ አስተሳሰቦችና አካሄዶች የተበከለ በመሆኑ ከመሬት ላይ ካለው መሪር ሃቅ ለሚነሱ (ለሚሰነዘሩ) እጅግ አስፈላጊና ፈታኝ ጥያቄዎች የሚሰጣቸው ምላሾችም በዚያው ልክ በሸፍጥና በሴራ የተሞሉና ከእውነታው ጋር የማይገናኙ ናቸው። እንዲህ አይነቶች አስከፊ አስተሳሰቦችና አካሄዶች ደግሞ የተጠናወጡት የተወሰኑ ባለሥልጣናትን ወይም የመንግሥትና የፓርቲ አካላትን ብቻ ሳይሆን እራሱን ሥርዓቱን ነው ከላይ ከአናቱ እስከ ታች የእግር ጥፍሩ የተንሰራፉበትና ሥር የሰደዱበት ። ይህን ለማወቅ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ከላይ እስከታች ያሉ ባለሥልጣናት ፣ በሥራቸው የሚገኙ ሃላፊዎችና ካድሬዎች በየጊዜው የሚደሰኩሩትን ዲስኩርና የሚሰጡትን መግለጫ ወይም ሃተታ ወይም ማብራሪያ ከመሬት ጋር ካለው መሪር እውነት ጋር በማመሳከር ልብ ማለት ብቻ በቂ ነው። እርግጥ ነው እንኳን እንደ እኛ ባለ አገር
The post ጥያቄ፦ ከእኛ ለእኛ – ጠገናው ጎሹ appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.
ግንጥል ጌጥ በማንም አያምርም –ይነጋል በላቸው
በምሥጋናና አድናቆት ልጀምር፡፡ ሰው በሚሠራው መጥፎ ተግባር ከተወቀሰ በሚያበረክተው በጎ አስተዋፅዖም ሊመሰገንና አድናቆትም ሊቸረው ይገባል፡፡ ያስቸገረን የከንቱ ውዳሤ ሰለባዎች መብዛትና በጭብጨባ ናላቸው የሚዞር ባለጊዜዎች በወር ተራ የሚሰነዝሩብን ያልተገባ እርግጫ ነው፡፡ ዛሬ ዕለቱ ሰኞ ነሐሴ 11 ቀን 2012 ዓ.ም ነው፡፡ ባሳለፍኳት ሌሊት ኢትዮ360 ዩቲዩብ ላይ ከአንድ ዕውቅ ኢትዮጵያዊ ለዶክተር አቢይ የተላከ ግልጽ ደብዳቤ ሲነበብ ሰማሁ፡፡ ሰሚ ቢገኝ ድንቅ ወቅታዊ መልእክት ነው፡፡ “ምክር የድሃ ነበርሽ፣ ማን ቢሰማሽ” ይባላል፡፡ ድህነት ሲባል ደግሞ የሀብት ብቻ አለመሆኑን ልብ ይሏል እዚህ ላይ፡፡ ቤት ሙሉ ገንዘብ እያለህም በአንድ ወይ በሌላ ነገር ድሃ የምትሆንበት አጋጣሚ ሞልቷል፡፡ … ያ ታዋቂ ሰው በኔ የልጅነት ዘመን እጅግ መሳጭ የፕሮቴስታንት መዝሙሮችን ሲያሰማንና
The post ግንጥል ጌጥ በማንም አያምርም – ይነጋል በላቸው appeared first on ዘ-ሐበሻ (ZeHabesha) Latest Ethiopian News Provider 24/7.