Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ተናገር መጣጥፍ (ዘ-ጌርሣም)

$
0
0

ተናገር ማህደር ተናገር ዝክሩ በዚያች በኛ ሀገር ከቀየ እስክ ደብሩ ተናገሪ ቋራ አንች ትንሽ ሰፈር ማነን አንደወለድሽ ያስከበረ ሀገር ተናገሪ ደግመሽ ማን እንደገደለው የት ላይ እንደሞተ ለምንስ ሽጉጡን ወደ አፉ ከተተ ተናገር መተማ አንት ጨካኝ በረሃ ጀግናችን ያስቀላህ ሳታጠጣ ውኃ አንተ አውሊያም በረሃ ለድርቡሽ ያደላህ የቅዱሱን ንጉሥ አንገት ቆርጠህ በላህ የታሪክን መድበል በእሣት አስለበለብህ ተናገር አድዋ ሣልሳዊ ግፉን በምድር በሰማይ ወገን መደብደቡን ለሦስቱ ቀለማት ለኢትዮጵያ ባንዲራ ጀግና እንደ ጧፍ ሲቀልጥ ለሞቱ ሳይፈራ ጠላት አፍሮ ሲሄድ በምኒልክ ተራ ተናገር አድዋ ስንቱ ጀግና ሞቶ ስንቱ ተረፈልህ ባትናገር አንኳን መመዝገብ አለብህ ስማቸውን ዘርዝር በማዕረግ ለይተህ ተናገር ሳትደብቅ የሆነውን ሁሉ ምስክሮች የሉም አልቀዋል በሙሉ

The post ተናገር መጣጥፍ (ዘ-ጌርሣም) appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.


“የክልልነት ጥያቄ ያላቸው ከሲዳማ የትግል ሂደት ውጤቱን ብቻ ሳይሆን ውድቀትንም መማር አለባቸው”አቶ ደስታ ለዳሞ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር

$
0
0

• ሲዳማ በትግል ባለፈበት መንገድ አንዴ ሲወድቅ ሌላ ጊዜ ሲነሳ ቆይቶ ነው እዚህ ሊደርስ የቻለው። ስለዚህም መማር ካለብን ከጥንካሬም ከድክመትም ነው። ምናልባት ይጠቅማል ብለን ካሰብን ደግሞ ጥንካሬውን ይዘን መቀጠል እንችላለን። ድክመቱን ግን መድገም አይኖርብንም። ሞኝ ከራሱ፤ ብልህ ደግሞ ከሰው ይማራልና። • እኛ አሁን ክልል ስለሆንን ምንም ጥያቄ የለንም፤ ትግልም የለም ማለት አይደለም። ሲዳማ ክልል ሆነ ሲባል የሆነ ሰፈር ደግሞ እኔ ዞን ካልሆንኩ የሚል ጥያቄ ከወዲሁ ቀጥሏል። አንዳንድ ቀበሌዎች ደግሞ ተሰብስበው እኛ ወረዳ እንሆናለን ብለዋል። ስለዚህ አይነቱ ይቀያየር እንጂ ትግሉ በየወረዳው አለ። እነዛ ትግሎች ደግሞ ወደቅራኔ ተቀይረው ቅራኔው ለጠላት ምቹ ሁኔታ ቢፈጥርና ጫጫታው ቢበዛ እንዲሁም ቢሰፋና ቢቀጥል ወደሁከትና ቀውስ ነው የሚያመራው።

The post “የክልልነት ጥያቄ ያላቸው ከሲዳማ የትግል ሂደት ውጤቱን ብቻ ሳይሆን ውድቀትንም መማር አለባቸው”አቶ ደስታ ለዳሞ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

የከተማዋ ነዋሪዎች ለሰላም ከመንግሥት ጎን እንደሚሆኑ ገለጹ

$
0
0

መምሩ ዋሲሁን የአዲስ አበባ ነዋሪ ናቸው። ወልደው ከብደው የልጅልጅ አይተው 60 ዓመት በዚህች ምድር ሲኖሩ በዕድር፣ በዕቁብ፣ ዘመድ ለማፍራት ልጃቸውን ክርስትና ሲሰጡ፣ እርሳቸውም ለዝምድና ተፈልገው ክርስትና ሲሰጣቸው፣ አማች እና ምራት ሲሆኑ በሌላም ማህበራዊ ግንኙነት በጉርብትና አብረዋቸው ከኖሩት ጋር በዘርና ሐረግ ሳይሆን ሰው በመሆናቸው ብቻ ተሳስበው፣ ተከባብረውና ተዋድደው እንደኖሩ ይናገራሉ። እርሳቸው በዕድሜያቸው የሚያውቁት ኦሮሞ በጉዲፈቻ ልጅ ሲያሳድግ። ያሳደገውንም ከወለደው ልጅ እኩል ሲያደርገው ነው። በዚህ የሚያውቁት ኦሮሞ ዛሬ የሰው ህይወት ሊያጠፋ ተነሳ ሲባል መስማታቸው እንግዳ ነው የሆነባቸው። ወንድም በንወድሙ ላይ መነሳቱ፣ አብሮ የኖረን ሰው ለማለያየትና ለውጭ ጠላት አሳልፎ ለመስጠት የሚደረግ ጥረት የኢትዮጵያውያን ድርጊት ነው ብለው ለመቀበልም ይቸገራሉ። በየጊዜው የሚነሱ ሁከትና ግርግሮችንም አጥብቀው ይቃወማሉ።

The post የከተማዋ ነዋሪዎች ለሰላም ከመንግሥት ጎን እንደሚሆኑ ገለጹ appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

የኦፌኮ አመራራር አቶ በቀለ ገርባና አቶ ጃዋር መሃመድ ፍርድ ቤት ቀረቡ

$
0
0

የአርቲስት ሀጫሉ ግድያን ተከትሎ አስክሬን በመቀማት እና ሁከት በመፍጠር ወንጀል የተጠረጠሩት አቶ ጃዋር መሃመድና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ ሌሎች ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀርበዋል። አቶ ጃዋር መሃመድ እና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ ሌሎችም ተጠርጣሪዎች በዛሬው እለት ነው ልደታ ምድብ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት እና አራዳ ምድብ ተረኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት። ፍርድ ቤቱ ከድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ ከተከሰተው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ ከሁለት ሳምንት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት የአቶ ጃዋር መሐመድን ጉዳይ ተመልክቷል። አቶ ጃዋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ፖሊስ የጀመረውን ምርመራ ለማጠናቀቅ ተጨማሪ ቀናት እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል። ይህንንም ተከትሎ የጃዋር ጠበቃ ደንበኛቸው በዋስ

The post የኦፌኮ አመራራር አቶ በቀለ ገርባና አቶ ጃዋር መሃመድ ፍርድ ቤት ቀረቡ appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

የታላቁ ሕዳሴ ግድብን አስመልክቶ የሚደረጉ ድርድሮች እንደሚቀጥሉ የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ

$
0
0

የታላቁ ሕዳሴ ግድብን አስመልክቶ የሚደረጉ ድርድሮች የኢትዮጵያን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ እንደሚቀጥል የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ የምታደርገው ድርድር የአሁኑን ትውልድ ብቻ ሳይሆን የመጪውን ትውልድ ጥቅም በሚያስጠብቅ መልክ የሚደረግ እንደሆነም ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ጨምረው ገልፀዋል። ዘግይቶ የነበረው የግድቡ የብረት ሥራ እና የጄኔሬተር ተከላ አሁን ላይ ተሠርቶ አልቋል ያሉት ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፣ በዘንድሮው ዓመት የግድቡን ከፍታ ከ525 ወደ 560 ማምጣት መቻሉን ጠቁመዋል። ባለፈው ዓመት ውኃው ያልፍ የነበረው በ525 ከፍታ ላይ እንደነበር፣ አሁን ግን 560 ከፍታ ላይ ከደረሰ በኋላ የሚያልፍ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ከ560 ከፍታ በታች ያለው ውኃ ግድቡ ውስጥ የሚቀር እንደሆነ እና

The post የታላቁ ሕዳሴ ግድብን አስመልክቶ የሚደረጉ ድርድሮች እንደሚቀጥሉ የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

የኢትዮጵያውያን ሰላማዊ ሰልፍ በጄኔቫ

$
0
0

ይህንኑ ጥሪያቸውን የገለጹባቸውን ደብዳቤዎችም ለተመ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እና ለሌሎችም የተመድ ተቋማት አስገብተዋል።ሰልፈኖቹ ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዓቢይ አህመድም ደብዳቤ ልከዋል። በደብዳቤው መንግሥት ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ የደረሰውን ጥፋት ለማስቆም ፈጣን እርምጃ ባለመውሰዱ ቅሬታቸውን ገልጸዋል። ስዊዘርላንድ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ዛሬ ጄኔቭ በሚገኘዉ የተባበሩት መንግሥታት ጽፈት ቤት እንዲሁም በሰብዓዊ መብቶች ተቋማት ፊት ለፊት ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ  ኢትዮጵያ ዉስጥ በአርቲስት ሃጫሉ ግድያ ሰበብ በግፍ ግድያ የፈፀሙ እና ንብረት ያወደሙ ግለሰቦች ለፍርድ እንዲቀርቡ ፤ ተጎጅዎችም ፍትህ እንዲያገኙ ጠየቁ። ዶቼቬለ ያነጋገራቸው ሰልፉ አዘጋጆች ፣የሃይማኖት እና የዘር ጥላቻን  የማያካሂዱ ተቋማትም ሆነ ግለሰቦች ለፍርድ እንዲቀርቡ ጥሪ አስተላልፈዋል። ይህንኑ ጥሪያቸውን የገለጹባቸውን ደብዳቤዎችም ለተመ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እና

The post የኢትዮጵያውያን ሰላማዊ ሰልፍ በጄኔቫ appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

ይድረስ ለክቡር ጠቅላይሚር አብይ አህመድና የማያልፍ ታሪክ ሠርተው ማለፍ ለሚሹ ጓደኞችዎ (ሰዉነት ደሃብ ከሃገረ ስዊድን)

$
0
0

አብይ ተሰማራ – – – አብይ ተሰማራ እንደ አብርሃም ሊንከን – – – እንደ ቼጉቬራ ከገፊዎች ሳይሆን – – – ከተገፉት ጋራ ሊገፉም ከታጩት – – – ያገርልጆች ጎራ ካፍንጫ ሥር ሳይሆን ሩቅ ከሚያልሙ – – – ቀና ልብ ያላቸው ጥቂት ጓዶች ጋራ   ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ በአሁኑ ወቅት ሃገራችን የገባችበት ሲያዩት ቀላል የሚመስል ነገርግን እጅግ አደገኛ አጣብቂኝ ነው :: አሁን ያለንበት አጣብቂኝ አንድ በሥልጣን ላይ ያለ አካል  ከሚያጋጥሙት ዕድሎች አንጻር ከታየ በጣም በተወሰነ  ደረጃ ከ 1997 ምርጫ ማግስት ጋራ ሊመሳሰል የሚችል ነው :: ከሚያመጣው አደጋ አንጻር ካየነው ግን የአሁኑ እጅግ በብዙ እጥፍ የከፋና ምናልባትም የአመራር መሪዉን ያያዛችሁት ሠዎች

The post ይድረስ ለክቡር ጠቅላይሚር አብይ አህመድና የማያልፍ ታሪክ ሠርተው ማለፍ ለሚሹ ጓደኞችዎ (ሰዉነት ደሃብ ከሃገረ ስዊድን) appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

ከሽብሩ ጀርባ ጀርባ –አሁንገና ዓለማየሁ

$
0
0

ሰሞኑን በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ስለተከስተው የሽብርና የሰቅጣጭ ጭካኔ ድርጊት በተለያዩ የመገናኛ ብዙኅን ግልብ ትንታኔዎች ሲሰጡ ይስተዋላል። የነዚህ ትንታኔዎች ግልብነት የመነጨው ሽብሩን በነጠላው ከሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ አኳያ ብቻ ለመረዳት ከመሞከር ይመስለኛል። እርግጥ ለሽብሩ ሰፈርኛ ምክንያት ስነፈልግለት ሕወሓት በለሆሳስ ወደ ነጻ ሀገረ መንግሥት ለሚያደርገው የጨለማ ግስጋሴ ትኩረት ማስቀየሻ ተኩስ ነው ልንል እንችላለን። ያስኬዳልም። ሽብር ግን በዓለማችን ላይ ታላላቅ የኢኮኖሚ እና ጂኦ ፖለቲካዊ ጥቅሞችን ለማራመጃ በረቀቀ ስልት የሚተወን ብዙ ተዋናዮች፣ የመድረክ ቅንብር መሪዎችና ጸሐፌ ተውኔቶች ያሉበት ክሥተት ነው። ሽብርን ቅኝ ገዢዎች፣ የእጅ አዙር ቅኝ ገዢዎችና የነርሱም አሻንጉሊቶች ጭምር ትላልቅ ጥቅሞቻቸውን ለማስከበሪያ የተጠቀሙበት፣ በዘመናትም እጅግ ያራቀቁት መሣሪያ ነው። የሽብር አጠቃቀም ዋና መለያው የሽብሩ ዋና

The post ከሽብሩ ጀርባ ጀርባ – አሁንገና ዓለማየሁ appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.


ከውጭ የሚመጣ መንገደኛ በ72 ሰዓታት የሚጠበቅበት የኮሮናቫይረስ ምርመራ ማረጋገጫ ወደ አምስት ቀን ከፍ ተደረገ

$
0
0

ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣ መንገደኛ በ72 ሰዓታት ውስጥ ተመርምሮ ‘‘ከኮሮናቫይረስ ነፃ’’ የሚል ማረጋገጫ እንዲያመጣ የሚያስገድደው መመሪያ ወደ አምስት ቀናት ከፍ መደረጉን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። የሚኒስትሮች ኮሚቴ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅታዊ ሁኔታና ቀጣይ አዝማሚያ፣ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም እንዲሁም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ዛሬ ተወያይቷል። ከዚህ ቀደም ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣ ማንኛውም ዜጋ በ72 ሰዓት ጊዜ ውስጥ ተመርምሮ ከቫይረሱ ነፃ የሚል ማረጋገጫ ሲኖረው ወደ መግባት እንደሚችል ነገር ግን በቤቱ ለ14 ቀናት እንደሚቆይ የሚደነግግ መመሪያ ወጥቶ ነበር። ከውጪ የሚመጡ ዜጎች የምርመራ ውጤት ካልያዙ ለሰባት ቀን ወደ ለይቶ ማቆያ እንደሚገቡም ይታወቃል። ዛሬ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳስታወቁት በበርካታ አገራት ምርመራው ጊዜ የሚወስድ እና

The post ከውጭ የሚመጣ መንገደኛ በ72 ሰዓታት የሚጠበቅበት የኮሮናቫይረስ ምርመራ ማረጋገጫ ወደ አምስት ቀን ከፍ ተደረገ appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

የዲሲ ሰላማዊ ሰልፍ ሐምሌ 16, 2020

ሪያል ማድሪድ 34ኛ የላ ሊጋ ዋንጫውን አሸነፈ

$
0
0

ትናንት ምሽት በተደረጉ የ37ኛ ሳምንት የላ ሊጋ ጨዋታዎች ሪያል ማድሪድ ቪላሪያልን አስተናግዶ 2 ለ 1 በማሸነፍ አንድ ቀሪ ጨዋታ እያለው 34ኛ የላሊጋ ዋንጫውን አሸንፏል፡፡ በምሸቱ በተከናወነው ጨዋታ ለሪያል ማድሪድ ሁለቱንም የማሸነፊያ ግቦች ካሪም ቤንዜማ ነው ያስቆጠረው፡፡ ከተከታዩ ባርሴሎና በሰባት ነጥብ ልዩነት የዋንጫ ባለቤት መሆኑን ያረጋገጠው ማድሪድ ከሶስት አመታት በኋላ የላ ሊጋ ዋንጫ ከፍ ማድረግ ችሏል፡፡ ባለፉት ሶስት አመታት የላሊጋው የበላይ የነበረው ባርሴሎና በምሽቱ ጨዋታ በሜዳው በኦሳሱና ሁለት ለአንድ ተሸንፏል፡፡ ከድሉ በኋላ አሰልጣኝ ዚነዲን ዚዳን በሰጠው አስተያየት ከሶስት ዓመታት በኋላ ከማድሪድ ጋር ላ ሊጋን ማሸነፉ ከሻምፒዮንስ ሊግ ድል በላይ እንዳስደሰተው ገልጿል፡፡ ” ይህ ድል ከምንም በላይ ነው ያለው አሰልጣኝ ዚዳን ዋንጫውን

The post ሪያል ማድሪድ 34ኛ የላ ሊጋ ዋንጫውን አሸነፈ appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በአርቲስት ፈቃዱ ተክለ ማርያም ዙሪያ ቴዲ ተሾመ ስም ጠርቶ እውነቱን አፈረጠው

የዘር ፍጅቱ በነፃና ገለልተኛ አጣሪ ኮሚሽን ይጣራ!!! –ፀ/ት ፂዮን ዘማርያም

$
0
0

ኢት-ኢኮኖሚ            /ET- ECONOMY የህወሓት፣የኦነግ ቄሮ፣ ኦነግ ሸኔ፣ ኦፌኮ ድርጅታዊ የዘር ፍጅት!!! ‹‹የሃጫሉን ሞት ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በብሔር እና ሃይማኖት ማንነት ላይ ያነጣጠረና በዘር ተኮር ጭፍጨፋ ሊፈረጅ የሚችል የጥቃት እርምጃ በተደራጁ እና በታጠቁ ኃይሎች  መፈጸሙን የሚያሳዩ ማስረጃዎች ከተለያዩ አቅጣጫዎች በመውጣት ላይ ናቸው። አንዳንድ የመንግስት አካላትም በዚህ ጥቃት ዙሪያ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተሳትፎ እንደነበራቸው በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር ተገልጿል። በአንዳንድ ስፍራዎችም የክልሉ ታጣቂዎች መሳሪያቸውን ጭምር በሕዝብ ላይ ጥቃት ይፈጽሙ ለነበሩት ቡድኖች አሳልፈው በመስጠት ጥቃቱ እንዲፈጸም መደረጉም ተገልጿል። ይህም ብቻ አይደለም በበርካታ የኦሮሚያ ከተሞች ዘር ተኮር የሆነው ጥቃት እና ጭፍጨፋ ሲፈጸም በአካባቢው የነበሩ የመንግስት ባለሥልጣናት እና የጸጥታ ኃይሎች ዳር ቆመው ጭፍጨፋውን፣ የንብረት ማውደሙት

The post የዘር ፍጅቱ በነፃና ገለልተኛ አጣሪ ኮሚሽን ይጣራ!!! – ፀ/ት ፂዮን ዘማርያም appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

በየአካባቢያችን የሚገኙ የግጭት ነጋዴዎችን በጋራ እንክላከል –የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት

$
0
0

ሙሉ መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል:- የተከበራችሁ የሀገራችን ሕዝቦች፣ ክቡራትና ክቡራን ባለፈው ሰሞን የአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳን ሞት ተከትሎ ግጭት ጠማቂዎች ባስነሡት ሑከት አያሌ ወገኖቻችን ሕይወታቸው አልፏል፤ የጸጥታ አካላት ተገድለዋል፡፡ በመቶ ሚሊየኖች የሚቆጠር የግለሰቦች፣ የሕዝብና የመንግሥት ንብረት ወድሟል፡፡ በቅድሚያ በሑከቱ ሕይወታቸው ላለፈው ወገኖቼ የተሰማኝን ኀዘን መግለት እወዳለሁ፡፡ ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናትን እመኛለሁ፡፡ መንግሥት ከማኅበረሰቡ ጋር በመሆን የተጎዱትን ለማቋቋም እንደሚሠራ፤ ወንጀለኞቹንም ለፍርድ የማቅረቡን ሂደትና የሕግ የበላይነትን ማስከበሩን እንደሚቀጥል በዚሁ አጋጣሚ በድጋሚ ላረጋግጥላቸው እወዳለሁ፡፡ ሁላችንም እንደምናውቀው የፖለቲካ መዝገበ ቃላችን የተሞላው ‹ምታው፣ ደምስሰው፣ ቁረጠውና ፍለጠው› በሚሉ የሞት ቃላት ሲሆን በመሳደድና ማሳደድ ዙሪያ መሽከርከር ከጀመረ ዘመናት ተቆጥረዋል። “ድርጊት ሲደጋገም ልማድ ይሆናል” እንዲሉ አሁን ያለው የፖለቲካ ባህላችን የተቀዳው ባንድ ወቅት

The post በየአካባቢያችን የሚገኙ የግጭት ነጋዴዎችን በጋራ እንክላከል – የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

በውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያውያን ከግጭት አነሳሽ መልዕክቶች ይልቅ ለአገር ሰላምና አንድነት እገዛ ማድረግ ይኖርባቸዋል –ኦባንግ ሜቶ

$
0
0

በውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያውያን ከግጭት አነሳሽ መልዕክቶች ይልቅ ለአገር ሰላምና አንድነት እገዛ ማድረግ ይኖርባቸዋል – ኦባንግ ሜቶ አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2012 (ኢዜአ) “በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አገር ውስጥ ያለውን ህዝብ “ተነስ ውጣ” ከሚሉ የግጭት አነሳሽ መልዕክቶች ይልቅ ለአገር ሰላምና አንድነት የሚጠቅሙ ስራዎች ላይ እገዛ ማድረግ ይኖርባቸዋል” ሲሉ የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ኦባንግ ሜቶ ተናገሩ። በተለያዩ አለም አገሮች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለአገሪቱ ልማት፣ ዴሞክራሲና ሰላም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረጉ ይገኛሉ። በዚያው ልክ በአገሪቱ ያለውን ሰላም ለማደፍረስ ከውጭ ሆነው ‘ተነስ ውጣ’ የሚል ግጭት ቀስቃሽ መልዕክት በማስተላለፍ ስራ ላይ የተጠመዱ ጥቂት ሃይሎች መኖራቸው ግልጽ ነው። የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ኦባንግ ሜቶ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ግጭት የሚቀሰቅስ

The post በውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያውያን ከግጭት አነሳሽ መልዕክቶች ይልቅ ለአገር ሰላምና አንድነት እገዛ ማድረግ ይኖርባቸዋል – ኦባንግ ሜቶ appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.


ውሃ ለኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ የማይተካ ሚና ያለው ውድ ሃብት በመሆኑ ሁሉም በአግባቡ መጠበቅና መጠቀም እንዳለበት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዓቢይ አህመድ ገለጹ

$
0
0

1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የውሃ መሳቢያ ሞተር ፓምፖች ለሁሉም ክልሎች ማከፋፈል ጀምሯል። የውሃ፤ መስኖና ኢነርጂ እንዲሁም የግብርና ሚኒስቴሮች በጋራ በመሆን የኮሮና ወረርሸኝ በግብርናው ዘርፍ ሊያስከትል የሚችለውን ተጽዕኖ መቀነስና ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የውሃ መሳቢያ ሞተር ፓምፖችን ለሁሉም ክልሎች አከፋፍለዋል። ከፓምፖቹ በተጨማሪም ለሁለተኛው የከተሞች የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ድጋፍ የሚሆኑ ተሽከርካሪዎች ለክልሎቹ ተሰጥተዋል። በርክክቡ ሥነ-ሥርዓት ላይ የክልል የሥራ ኃላፊዎችና ተወካዮች ተገኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በዚሁ ጊዜ ውድ የተፈጥሮ ሃብት የሆነውን ውሃ በአግባቡ ማመንጨት፣ መጠበቅና መጠቀም ይገባል ብለዋል። ውሃ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ የዓለም የዲፕሎማሲና የግጭት መነሻ እንደሚሆን ገልጸው፣ ይህን ውድ የተፈጥሮ ሃብት መጠበቅ ግዴታ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተውታል። የኢትዮጵያ ዋነኛ የውሃ

The post ውሃ ለኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ የማይተካ ሚና ያለው ውድ ሃብት በመሆኑ ሁሉም በአግባቡ መጠበቅና መጠቀም እንዳለበት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዓቢይ አህመድ ገለጹ appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

የጽንፈኞች ጸሃይ እየጠለቀች ይሆን? –መሳይ መኮነን

$
0
0

አዲስ አበባና አዳማ። ኦቢኤንና ዋልታ። በዚህ ሳምንት ያወጧቸው ዘጋቢ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ምናልባትም ማርሽ ቀያሪ ሊሆኑ ይችላሉ ብሎ መገመት ስህተት አይደለም። ሁለቱም ፕሮግራሞች፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት ኢትዮያን በዋናንትም የኦሮሚያን ክልል ዘቅዘው የያዙ፡ ሰላምና መረጋጋት ያሳጡ፡ በአንድም ይሁን በሌላ የፌደራሉን መንግስት አስወግዶ በተረኝነት ስካር ውስጥ የተዘፈቁ ጽንፈኛ ሃይሎችን ከአራት ኪሎ ቤተመንግስት ለማንገስ ግብ አድርገው ታላቁን ጥፋት አውጀው የተነሱ ሃይሎችን በጨረፍታ ያጋለጡ ናቸው። ባለፈው ረቡዕ ምሽት በኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ የተሰራጨውና የሰው ልጅ ጭካኔ እስከየት ጥግ ሊደርስ እንደሚችል የታየበት አስጨናቂ አሰቃቂ ትዕይንቶች የበዙበት ፊልም ለህዝብ ቀርቧል። ከዚያ ቀደም ብሎ በዋልታ ቴሌቪዥን በአንድ ባለሀብት ግፍ ተፈጸመብን ያሉ ግለሰቦች አቤቱታ እንዲሁም ባለሀብቱ የሀገርና የህዝብ ሀብትን ላይ

The post የጽንፈኞች ጸሃይ እየጠለቀች ይሆን? – መሳይ መኮነን appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

ሥጋ አማረው ሆዴን (ዘ-ጌርሣም)

$
0
0

ሥጋ አማረው ሆዴን ሥጋ የት ተገኝቶ አንተ ትብስ አንች በተባባሉበት ክፉ ቀን ሲመጣ አብረው በቆሙበት በደጎቹ ዘመን በቁርጡ ተበልቶ የሙክት የጠቦት ብሎ እንዳልመረጠ ጎረቤት ሰብስቦ ዘመድ አዝማድ ጋብዞ ቀይና አልጫውን አስፈትፍቶ አቅርቦ ዱለትና ጥብሱን እንዳላስመረጠ ሥጋ አማረው ሆዴን ብዙ የለመደው የዶሮዋን አንኳን ማጣቱ ሳይገባው ድንችና ጎመን ፓስታ መኮሮኒ ፓስቲና ሳንድዊች ሾርባ ሚንስትሮኒ ቃሪያና ቲማቲም የአትክልት ዘር በሙሉ የሆቴሎች ምግብ ባለዘመኖቹ አጠፉት ሥጋውን ከሽንጥ እስከወርቹ ሥጋ አማረው ሆዴን ሥጋ የት ተገኝቶ በደጎቹ ዘመን በቁርጡ ተበልቶ አረ ሥጋ አምሮኛል ሥጋ ፈልጉልኝ ባይሆን ለአዲሱ ዓመት ለባዕሉ ቢሆነኝ የግጦሹ ሜዳ ታርሶ በመድረቁ ሥጋ ያስለመዱኝ ከብቶቹም አለቁ ክትክታና ወይራ የደጋው አትክልት አድልቦ እሚያሳድግ ሙክት ከጠቦት

The post ሥጋ አማረው ሆዴን (ዘ-ጌርሣም) appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዛሬ በለንደን ከተማ ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ

$
0
0

መንግሥት በወንጀለኞች ላይ ተገቢ እርምጃ እንዲወስድ ተጠየቀ መንግሥት የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ሞት ተከትሎ በኢትዮጵያ በግፍ ግድያ የፈፀሙ እና ንብረት ያወደሙ ግለሰቦችን ለፍርድ እንዲያቀርብ ተጠየቀ። ተጎጅዎችም ፍትህ እንዲያገኙ ተብሎአል። በብሪታንያ መዲና ለንደን ላይ የተደረገዉን ሰልፍ የጠራዉ የኢትዮጵያዉያን ትብብር በብሪታንያ በሚል የተደራጀ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ አአካል ነዉ በብሪታንያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዛሬ በለንደን ከተማ ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ በድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ሰበብ ሰዎችን በገደሉ ንብረት ባወደሙና በዘረፉ ዜጎችንም ባፈናቀሉ ላይ መንግሥት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ ጠይቁ።መንግሥት ለተጎጂዎች አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያደርግም ጥሬ አቅርበዋል። መሰል ድርጊቶች ወደፊት እንዳይፈጸሙም መንግሥት የዜጎችን ደህንነት በአግባቡ እንዲጠብቅም ጠይቀዋል።መንግሥት ይወስዳል ያሉትን ሕጋዊ እርምጃ እንደሚፈግፉም ሰልፈኞቹ አስታወቀዋል። ጥሪዎቻቸውን የያዘ ደብዳቤ በኢትዮጵያ

The post ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዛሬ በለንደን ከተማ ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

በዋሺንግተን ዲሲ ስለተደረጉ ሰልፎች

$
0
0

 ዋሽንግተን ዲሲ — ዛሬ በዋሺንግተን ዲሲ ከተማ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁለት ሰላማዊ ሰልፎች አድርገዋል። የመጀመሪያው ኢትዮጵያ ውስጥ ከሰሞኑ የደረሰውን የሕይወት እና ንብረት ውድመት የሚያወግዝ እና የጠ/ሚ አቢይ አህመድ አስተዳደር ሕግን ለማስከበር እየወሰደ ነው የተባለውን ርምጃ ለመደገፍ የተጠራ ነው። ሁለተኛው ደግሞ ከተለያዩ የዩናይትድ ስቴትስ ግዛቶች እንደመጡ የሚናገሩ ወጣቶች፣ የታሠሩ የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ፣ ከእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ጋር በመገኘታቸው ብቻ ያለ ጥፋታቸው የታሰሩ ሦስት የአሜሪካ ዜጎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እና ኢትዮጵያ ውስጥ የተፈፀመው የሰብዓዊ መብት ጥሰት በገለልተኛ አካል እንዲጣራ የሚጠይቅነው። የሁለቱንም ሰልፎች አስተባባሪዎች ዘገቢዎቻችን አነጋግረዋቸዋል። ሀብታሙ ስዩም የመጀመሪያውን ሰልፍ ፣ጽዮን ግርማ ደግሞ ሌላኛውን ሰልፍ ይዘቶች አከታትለው ያሰሙናል። VOA Amharic

The post በዋሺንግተን ዲሲ ስለተደረጉ ሰልፎች appeared first on ዘ-ሐበሻ: ZeHabesha Latest Ethiopian News Provider.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>