Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

በሶማሊያ ሕይወቱን እየገበረ የሚገኘው ሰራዊት ላለፉት 6 ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈለው ታወቀ

$
0
0

27210718553_d292423c53_z

(ዘ-ሐበሻ) አልሸባብን ለመወጋት በሱማሊያ የሚገኘው የአፍሪካ ሕብረት ከ20 የማያንስ ሰራዊት ላለፉት 6 ወራት ምንም ዓይነት ደመወዝ እንዳልተከፈለው ቢቢሲ አጋለጠ::

አልሸባብን ለመዋጋት በሶማሊያ የሚገኘው ይኸው የኢትዮጵያን ጨምሮ የሌሎች አፍሪካ ሃገራትን ሰራዊት የያዘው እዚያው የሚገኘው የአፍሪካ ሕብረት ጦር በገንዘብ የሚደጎመው በአውሮፓ ህብረት የነበረ ቢሆንም የአውሮፓ ሕብረት ላለፉት 6 ወራት ገንዘብ እንዳልላከ ቢቢሲ ዘግቧል::

እንደ ቢቢሲ ዘገባ የአውሮፓ ሕብረት ለ እያንዳንዱ ሰራዊት በወር $1,028 ለመክፈል የተሰማማ ቢሆንም ወታደሮቹን ወደዚያው የሚልኩት ሃገራት $200 እንደሚቆርጡና ከሌሎች ክፍያዎች ተቆራርጦ ለወታደሮቹ $800 ዶላር ይደርሳቸዋል::

የአውሮፓ ሕበርት ገንዘቡን ላለፉት 6 ወራት ያልላከው በበሒሳብ ምክንያት ነው የሚል ድፍን ያለ ምላሽ ይሰጥ እንጂ በምን ዓይነት ሒሳብ ችግሩ እንደተፈጠረ የተባለ ነገር የለም::

ላለፉት 12 ወራት በአሚሶም ስር ያሉት የብሩንዲ; የዩጋንዳ; የኬንያና የኢቱኦጵያ ወታደሮች በአልሸባብ ጥቃት ሲደርስባቸው ቆይቷል::

ጁን 9 አልሸባብ 60 የኢትዮጵያ ወታደሮችን በሃልጋን መገደሉን; እንዲሁም ኤፕሪል 21 6 ወታደሮችን በቤይ አካባቢ መግደሉን መግለጹ ይታወቃል::
በተጨማሪም ፌብሩዋሪ 15 በሸበሌ አካባቢ 15 የኢትዮጵያ ወታደሮች በአልሸባብ መገደላቸው ተዘግቧል::

ይህንን ሁሉ የሕይወት መሰዋዕትነት የሚከፍልን ሃይል በሂሳብ ስህተት ደመወዝ ለ6 ወር መከልከልን ምን ይሉታል?


  የትግራይ ሰዎች ተፈናቀሉ:  አጉል  የወያኔ ጩኸት በሽንፋ-ጎንደር

$
0
0

tigrayላለፉት 40 ዓመታት አገርን  በማፈራረስ አባዜ  የተጠመደው  ወያኔ  በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ምክንያቶችን  በመፍጠር  ሲፈልግ  የትግራይ  ሕዝብ  ልጆቹን  ስለሰዋ  የትግራይ  ግዛት መስፋት አለበት፣ በሌላ  ጊዜ ደግሞ አባላቶቹን  አደራጅቶ  በተለያዩ   የሀገሪቱ  ክፍሎች በማስፈር፣ ብሎም  ከባንክ ብድር  በገፍ እንዲያገኙ በማድረግ  በሰፈሩባችቸው  አካባቢዎች ሁሉ  የንግድና  የእርሻ ሥራዎችን  በበላይነት እንዲይዙ አድርጓል። ስለሆነም  ወያኔዎች ተደራጂተው በሰፈሩባችው አካባቢዎች  ሁሉ  የአካባቢው ተወላጅ  በራሱ ቀዬ የበይ  ተመልካች  እንዲሆን  ተደርጓል ። በአጭሩ  ወያኔዎች ለ25 ዓመታት በመላ  ሀገሪቱ  የሚያካሂዱት  ዘረፋና የማያባራ የግዛት ተስፋፊነት ሌላው ቀርቶ በራሳቸው አምሳል የፈጠሯቸው  አጫፋሪ  የጎሣ  ድርጅቶች  እንኳ  ገደብ  የለሹን የወያኔ  ሁሉም  የኔ ይሁን በሽታ  ሥራ ላይ ለመትግበር ከአቅማቸው በላይ እየሆነ መጥቷል።

“<በጅብ  ጅማት  የተሰራ ክራር  ዜማው ሁልጊዜም  እንብላው> እንደሚባለው  ወያኔ ዛሬም እንዳመሰራረቱ ታላቋን  ትግራይ  የመፍጠር  በሽታው በተጠናከረ  መልኩ  ቀጥሏል። ወያኔ በጠባብነት ታዉሮ  አትዮጵያን  በስፋትና በአኩልነት ሊመራ  ቀርቶ እወክለዉ አለሁ የሚለውን  ትግራይን  እንኳ በአግባቡ በእኩልነት መወከል የተሳነው  የአንድ  አካባቢ ስብስብ  ነው፡፡. ለይስሙላ የትግራይ  ሕዝብ  ወኪል  ነኝ  ቢልም  እውነቱ  ግን በበላይነት እና በዋናነት የሚመራው  ከአርባ ዓመት በፊት አሽአ ማለትም አድዋ፣ ሽሬ፣ አክሱም ብሎ የመገንጠል ዓላማ አንግቦ  በሕቡእ  የተደራጀው ከሦስት አውራጃዎች በመጡ እጅግ በጣም ጠባብ  ግለሰቦች ሲሆን  ከኢትዮጵያ ጎሳዎች ያልተቀላቀልን  ‘ንጹሕ ትግሬ  እኛ  ነን የሚሉ በዝምድና  እና በጋብቻ የተሣሰሩ የአውራጃ አንጀኞች ናቸው።

ይህ የአሽአ  ቡድን  ምንም እንኳ  በታሪክ ስህተት የኢትዮጵያን  በትረ ሥልጣን  ቢይዝም  ሌት ከቀን ከተነሣበት ጠባብ  የአውራጃና የጎሣ ዓላማውን  አዉን ከማድረግ  ወደኋላ አላለም። ስለሆነም  እድገቱን  እና ሥልጣኑን  የሚገመግመው  የግል  ቴ  በሚለው  በትግራይ  የግዛት መስፋፋትና  ወያኔዎች ከሌላው ኢትዮጵያዊ  በላቀ  በሚያከማቹት  የሀብት መጠን  ነው።

አንገብጋቢዉና በማንም ኃይል ሊገታ የማይችለው  የወልቃይት  ሕዝብ  ጥያቄ  እየገፋ ከመጣ ወዲህ ደግሞ ወያኔ የብአዴንን  ባለመዋልነት  ጥያቄ  ውስጥ  አስገብቷል። ለዚህም  ነው  ሰሞኑን የወያኔ የስለላ ድርጅት ብዙ ከመከረ  በኋላ አዲስ ዐይን ያወጣ በጎንደር ሕዝብና  እንዲሁም በራሱ የበክር ልጅ ብአዴን ላይ ያነጣጠረ  ዘመቻ ከፍቷል።  ይህ ያልተጠበቀ  የወያኔ የትግራይ ሰዎች በጎንደር ተፈናቀሉ አዲስ ክስ አንዳንድ ጌቶች ለአሽከሮቻችው አመቺ እንዳልሆኑ  ሁሉ  ወያኔም  እንዲሁ ለብአዴን እና ለሚገዛው ሕዝብ  ያልተመቸ  ጌታ ሁኗል። ስለሆነም  የወያኔን  ገደብ የለሽ  ፍላጎት ማርካት ከማይቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል። ወያኔ ወልቃይትን ስጡኝ አለ፣ ወሰደም። ከዚያም ጠገዴን አምጡ አለ፣ ዝም ተባለ። ብሎም ዳንሻን፣ ሁመራን እስከ  ሱዳን ጠረፍ  ወሰደ፡፡ በወሎና እዲሁም  በአፋር ግዛቱን አስፍፍ።

“ወያኔ የትግራይ ሰዎች በጎንደር ሽንፋ  አካባቢ>  ተፈናቅለዋል  እናም  የበኩር ልጄ ብአዴን  የሰጠሁትን  የወያኔዎችን  የበላይነት  የማስጠበቅ  ኃላፊነት  አጓድሏል፣ ስለሆነም ብአዴንም  ሆነ የአካባቢውን  ሕዝብ እንቀጣለን  እያለ ነው። በውጭ ሀገርም ያሰማራቸው የታላቋ  ትግራይ  አቀንቃኞች  ኃላፊነት በጎደለው መልክ  የግል መንግሥታችን  የሚሉት ወያኔ በአፋጣኝ በብአዴን እና በጎንዳር ህዝብ  ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ከመወትወት አልፈው ገንዘብ በማሰባሰብ ላይ ናቸው።

የወያኔ ስልታዊ ተስፋፊነት-

  • በመጀመሪያ ከትግራይ ክልል ለሰፋሪነት መስፈርት  ያሟላሉ  የሚላችዉን ይመለምላል ፡፡ ከዚያም ሥልጠና ይሰጣል፣ ሥልጠናውም  በተናጠል  እና በቡድን  ለም በሆኑ  ሱዳንን በሚያዋስኑ  የኢትዮጵያ ይዞታዎች  አካባቢ በንግድና በእርሻ እንዴት አንደሚሰማሩ ፣ያደራጃል፡፡
  • ብአዴኖችን በቀጥታና  በሥውር ለወያኔ ሰፋሪዎች ሙሉ እርዳታ እንዲያደርጉ ይታዘዛሉ
  • ለተወሰኑ ተመልማዮች  ከፍተኛ  ገንዘብ  ለሥራ መቋቋሚያ  ከንድፈ ሃሳብ ጋር ይሰጣቸዋል
  • ለገሚሶች ደግሞ ያለ ቅድመ  ሁኔታ የባንኮች የመበደሪያ ሕግ  ተጥሶ  እስከ  5 ሚሊዮን ብር ድረስ እንዲበደሩ ይደረጋል።
  • ቀስ በቀስ ብዛት ያለው ወያኔ ከሰፈረና ሀብት ንብረት ካፈሩ  በኋላ <ማኅበረ ትግራይ> የሚባል ቡድን  ያቋቁማሉ፣ ከ30 በላይ አባወራዎች  ሲደርሱ  ደግሞ ከትግራይ ክልል በመጡ የወያኔ ባለሥልጣኖች  አዲስ አደረጃጀትና ሥልጠና ይሰጣቸዋል። ከገቢያቸውም ለትግራይ ክልል ግብር ይከፍላሉ።
  • ልጆቻቸው ትግርኛ እንዲማሩ መምህር  ከትግራይ  ያስመጣሉ
  • 50 አባወራዎች ሲደርሱ የራሳቸው ልዩ ዞን እንዲሰጣቸው ይጠይቃሉ

ለምሳሌ  በአብደራፊ ማለትም በታች አርማጭሆ ወያኔ የሠራው ቲያትር- በ1992-93 ደርግ እንደወደቀ በስደት ሱዳን ውስጥ ይኖሩ የነበሩ የትግራይ  ሰዎች ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ይመለሱ በሚል ዘይቤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሙሉ የገንዘብ ድጋፍ  30 አባወራዎች ለሱዳን ቅርብ  ለሆነችው አብደራፊ ላይ እንዲሠፍሩ ሆነ። የአካባቢው ሕዝብም ፣ እንኳን ደህና መጣችሁ ብሎ ተቀበላቸው፡፡ የመሬትም  ጥበት ስለሌለ  ሁሉም  መሬት አገኙ። ከድህነትም ተላቀቁ። ትንሽ ከቆዩ  በኋላ  ዘመዶቻውን  ከትግራይ  ማስመጣት ጀመሩ። የትግራይ  ሰዎች እየበረከቱ  መጡ፣ ከዚያም ለብአዴን ባለሥልጣናት ልዩ ዞን በአብደራፊ  ይፈቀድልን  ሲሉ ጠየቁ። ጥያቄው የአካባቢውን  ሕዝብ  አሳዘነ። ጉዳዩ ለአካባቢው ሕዝብ ብቻ ሳይሆን  በመላ  ክፍለ ሀገሩ  ከፍተኛ  ትዝብትና ቁጭት ፈጠረ። በእንግድነት  መቀበላችን  ቀያችን  ያስወስዳል  እንዴ?  ሲሉ  ራሳቸውን  ጠየቁ። እንዳዉም ጥያቄው  ከልዩ ዞን አልፎ   የቲ ፒ ኤል ኤፍ -TPLF/  የሕዝብ  ደህንነት ሠራተኛ  ዘፀአት  በሚል ቅጽል ስም <ታህታይ አርማጭሆ የሠፈሩ ትግሬዎች ወደ ትግራይ አስተዳደር መዛወር  አለባችው  ሲል አዲስ አጀንዳ ይዞ ብቅ አለ። አብደራፊ  የት ላይ እንደሚገኝ እና እንዴት ከትግራይ ጋር ሊተዳደር እንደሚችል  ጉግል ማፕ አይቶ የራስን  ፍርድ መስጠት ይቀላል።ይህ የወያኔ ተስፋፊነት  በሠፈራ ስም በመተማ፣ በሽንፋ፣ በኦሜድላ፣ በቤን-ሻንጉል (ጎጃም) እና በጋምቤላ እየተካሄደ  ነው።

ከላይ በተዘረዘሩት ምክንያቶች ሽንፋ ላይ በወያኔ ሠፋሪዎች እና በአካባቢው ሕዝብ  መካከል ልዩነቶች እየሰፉ መጡ።  በሠፈራ ስም የመጡት ወያኔዎች  ከጥቂት ዓመታት በኋላ  የአካባቢውን  ሕዝብ  እና  ብአዴን  የሚባለዉን  እንምራችሁ ማለት ጀመሩ። ብሎም –

  • በሠፋሪነት የመጡት ተቋቋሚ ሠፋሪዎች በቅጽበት ኢንቨስተሮች ናቸው ተብለው ከሠፈራ ወጥተው ከባንክ  በገፍ እንዲበደሩ ወያኔ አመቻቸ። የአካባቢው ሕዝብ  ከባንክ ብድር ለማግኘት ሲጠይቅ ከፈላጋችሁ   ወደ ቤን-ሻንጉል ሂዱና የእርሻ መሬትና የባንክ ብድር እንሰጣችኋለን ማለት ጀመሩ። ይህ እርምጃ ቀስ በቀስ የአካባቢውን  ተወላጆች ከአካባቢው በማስለቀቅ በምትኩ የወያኔ ሰዎችን ለማስፈር  ያሰበ ነው።
  • የወያኔ ሰዎች የሽንፋን ሕዝብ በእርሻ፣በጅምላ ንግድ፣ በችርቻሮ፣ በሆቴል  እና  በአራጣ አበዳሪነት  ከባንክ በተሰጣቸው ገንዘብ ሊያፈናፍኑት አልቻሉም። ስለሆነም የበላይነቱን  በአቋራጭ ተቆጣ ጠሩት፡፡.
  • በአካባቢው የሚገኘውን የደን  ሀብትም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የከስል  ፈቃድ በብቸኝነት በመያዝ  አካባቢውን  ወደ ምድረ-በዳነት ለወጡት።
  • የእጣን/ሙጫ ፈቃድ  ከወያኔ ሰዎች ውጭ እንዳይሰጥ አስከለከሉ፣ብሎም ያለአግባብ  በአምራች  ዛፎች ላይ  ጉዳት በገፍ አደረሱ፡፡   ዛሬ የአካባቢው የእጣን ዛፎች 60% መክነዋል።
  • የአካባቢውን የተፈጥሮ  የቀርቅሃ ሀብት ከሱዳን  ነጋዴዎች ጋር በመመሳጠር ወደሱዳን  በመላክ  እንዲጨፈጨፍ አድርገዋል።
  • በአካባቢው ወደ ሱዳን የአስመጭ እና የላኪነት የንግድ ፈቃድ ያለተወዳዳሪ እንዲይዙ ተደረገ።
  • ሽንፋ ውስጥ የሚኖሩ የትግራይ ሰዎች  የወያኔን ድርጅታዊ  መዋቅር  ዘረጉ።
  • ከትግራይ ክልል የመጡ የወያኔ አመራሮች በ6 ወር አንዴ ምስጢር በሆነ መልክ ለ3 ቀናት ሰሚናር ይሰጣሉ።
  • አብዛኛዎቹ ግብር በዛብን በማለት ለአካባቢው አስተዳደር ለብዙ ዓመታት ግብር መክፈል አቁሙ።
  • የቀበሌና የመንግሥት መሰብሰቢያ አዳራሾችን ያለቅድሚያ ጥያቄ በፈለጉበት ጊዜ የመስብሰብ መብት እንዲሰጣቸው ከመጠየቅ አልፈው ማሳፈራራት ጀመሩ።
  • የአካባቢን ጸጥታ በተመለከተ ሃላፊነት ይሰጠን  አሉ።
  • የአካባቢውን ሕዝብ እየሰለሉ ፀረ ወያኔ ናቸው ብለው የሚጠረጥሯቸውን ሰዎች ከትግራይ ክልል በመጡ የፀጥታ ኃይሎች አሳፍነው ወደ ትግራይ እንዲወሰዱ አደረጉ።
  • በወያኔ የበዓላት ቀን ላይ የትግራይን  ክልል ባንዴራ ማውለብለብ  ጀመሩ።
  • የወያኔ ምሥረታ በዓል በአካባቢው በሕዝብ  ዘንድ በብዓልነት እንዲከበር ጠየቁ ..ወዘተ።

በአጣቃላይ  ግንኝነቱ  የገዠና ተገዥ እየሆነ መጣ። ለሠፈራ  የመጡ ሰዎች አልፈው ተርፈው የፖለቲካውንና የኢኮኖሚውን  አውታር የግል አደረጉት።   የአካባቢው ሕዝብ ብአዴን ለሚባሉ የወያኔ አስፈጻሚዎች አቤቱታ  ቢያቀርብ  ሰሚ  ጠፋ። በዚሁ ያላሰለሰ የወያኔ ሠፋሪዎች በደል ምክንያት ተቃውሞው እየበረታ መጥቶ  የውስጥ እሳት ሆነ። ብሎም አመፅ ቀሰቀሰ። በተነሣው ተቃውሞ ድንጋይ በአንዳንድ ሱቆች ላይ ተወረወረ። ዘረፋ ግን አልተፈጸመም። የወያኔ ሠፋሪዎች <ጌታውን የተማመነ በግ..> እንዲሉ ለሳምንት ያክል ንብረታቸውን  ሳይከታተሉ  ሰነበቱ፡፡ ከዚያም የአካባቢውን  አስተዳደር አልፈው ወደ አዲስ አበባ  እና ባሕርዳር ጮኹ። የጠፋ ንብረት ካለ ዝርዝሩን  አቅርቡ  ሲባሉ ከነበራቸው ንብረት ከአሥር እጥፍ በላይ እንዲከፈላቸው ጠየቁ።  ብአዴንም ምንም ሳያቅማማ  ለመክፈል ከፍ ዝቅ እያለ  ነው።

አዉነቱ ይህ ሆኖ እያለ ተገልብጦ የአካባቢው ሕዝብ በበዳይነት ተፈርጆ የወያኔን ፍርድ እየጠበቀ ይገኛል። ወያኔዎች ተደፈሩ ቁጪት እና ትእቢታዊ  ጩኸት  ጎንደር፣ ባሕር ዳር፣  አዲስ አበባን አልፎ  የአድዋን  ከተማ  እያስፈከረ  ነው።  የወያኔ የአሁኑ የሽንፋ ጩኸት ዋና ዓላማው ወያኔን በመሸከም የጎበጠውን  አሮጌ  ብአዴንን አፈራርሶ  በአዲስ  ሹመኞች አመራር መቀየር ነው። ወያኔ ወልቃይት ላይ ያለበትን የሕዝብ ተቃውሞ  የትግራይ ሰዎች ተፈናቀሉ  በሚል ማምታታት  እና  ብአዴንን መብላት ነው። ለዚህ የወያኔ አዲስ እቅድ  በዋና አስፈጻሚነት ካሣ ተክለብርሃን  እና ዓለምነው መኮንን ተመልምለው አዲስ ቃለ መሓላ ፈጽመዋል። ውጤቱን በቅርቡ የምናየው ይሆናል። በአጎረስኩ እጄን ተነከስኩ እንደተባለው ለሠፈራ የመጣ ሕዝብ ያስፋሪውን ሕዝብ እጅ ሊነክስ አይገባም።   በደል በበዛ  ቁጥር በተቃራኒው አመፅን ይፈጥራል።  የሽንፋ አመፅ የዚሁ የተራዘመ የውያኔዎች የበደል ዉጤት ነው። በርግጠኝነት ግን የትግራይ ጥላቻ እንዳልሆነ ሙሉ በሙሉ መናገር የቻላል።

 

ሊቁ  እጅጉ

አዳነ አጣናው

6/27/2016

 

 

ለጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሮን… ከ ኢህአዴግ ጽህፈት ቤት;

$
0
0

ሰላም ክቡር ሚኒስቴር፤

abe-tokichaw-satenawህዝብዎ ባለፈው ባደረገው ምርጫ እርሶ የማይፈልጉትን መምረጡን ተከትሎ ስልጣንዎን ሊለቁ እንደሆነ በሰማን ግዜ በውነት ተደነቀን….
ለዚህ እኮ ነው እናንተ አውሮፓውያን ሁሌም የምትገርሙን፤ ሰልጠነናል አውቀናል ትላላችሁ እንጂ ገና ብዙ ይቀራችኋል። ሲጀመር ህዝቡ ድምጽ የሰጠው እርስዎ ከስልጣንዎ እንዲለቁ አይደለም፤ ቢሆንስ የምን ለህዝብ ፊት መስጠት ነው… በእንዲህ ያለው ሆድ የሚያስብስ ጊዜ የሚባለው ‘’ድርጅቴ ከፈቀደልኝ ስልጣኔን እለቃለሁ’’ ነው… ከዛ ስልጣንዎን ባይለቁም ድርጅታቸው አልፈቀደም ማለት ነው ይባላል።
ከሁሉ ከሁሉ ግን ህዝቡ ምን ሆንኩኝ ብሎ ነው እርስዎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የማይፈልጉትን እና ያልደገፉትን ነገር የሚፈልገው። አንዴ ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆኑ በኋላ እርስዎስ ህዝብን ማማከር ብሎ ፈሊጥ ከየት አመጡት? ዝም ብለው ያሻዎትን ወስነው ሲያበቁ… ህዝቡ እንዴት… ብሎ ሲጠይቅዎ ‘’ይሄንን ጉዳይ ለዚህ ህዝብ የማሳወቅ ግዴታ ያለብኝ አይመስለኝም።’’ ይባላል እንጂ ህዝብን ወስን ብሎ መጥራት ነውር አይደለም እንዴ…
እርግጥ ነው ህዝብ ባለጌ ነው አንዳንድ ጊዜም ሆ ብሎ ተቃውሞ ያስነሳ ይሆናል… ይሄንን መከላከል ታድያ ከባድ ነው ሊሉ ይሆናል እኮ… የሽብርተንነት አዋጅ አላችሁ አይደል እንዴ… እኛ ራሳችን እኮ አዋጁን ከናንተ ነው ቀጥታ ቃል በቃል የቀዳነው… ታድያ ከቃልዎ የሚያፈነግጠውን ሁላ ያፈነገጠውን ብቻ ሳይሆን ያሰበውን ሳይቀር የሽብርተኝነት አዋጁን እየጠቀሱ መጠፍነግ ሲችሉ… የምን ለህዝብ ፊት መስጠት ነው…. ?
እሺ እምቢኝ ብለው አንዳንድ ነውጠኞች ስራዎን ተቃውመው አደባባይ ወጡ እንበል… እንዲህ ያለ ነገር ሲገጥም በመጀመሪያ ደረጃ ማድረግ የሚገባዎ ሌሎች የርስዎ ደጋፊዎችን በቴሌቪዥን ጣቢያዎ አቅርበው ‘’አንዳንድ ጸረ ሰላም ሃይሎች የጠቅላይ ሚኒስትሩን መልካም ሃሳብ መቃወማቸው ተገቢ አለመሆኑ ተገለጸ’’ የሚል ዜና ማሰራት። (እንደውም የምን መልካም ሃሳብ ራዕይ ይበሉት እንጂ…) አዎ ‘’የጠቅላይ ሚኒስትሩን ራዕይ… (እንደውም የምን ጠቅላይ ሚኒስትር ብሎ ማቃለል ነው… (የታላቁን መሪ ይበሉት… ) አዎ ‘’አንዳንድ ጸረ ሰላም ሃይሎች የታላቁን መሪያችንን ራዕይ ለማደናቀፍ መሞከራቸው ተገቢ አለመሆኑን የለንደን ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ አክለውም ይህንን ታላቅ ራዕይ ለማደናቀፍ እና ህገ መንግስቱን በሃይል ለመናድ የሚሞክሩ የሻቢያ ተላላኪዎች ላይ መንስግስት አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን… ብለዋል።’’ ብሎ ዜና ማሰራት። (ያው የሻቢያ ተላላኪ ያልንልዎ ከተቸገሩ ይጠቀሙበት ብለን ነው ሰርተው ይከፍላሉ። የራስዎ ተላላኪ ሲያገኙ ይመልሳሉ) እኛ ኦነግ ኦብነግ ግንቦት ሰባት እና ሌሎችም ስላሉን ችግር የለውም።
ከዛ ህዝቡ በዜና እርምጃ ይወሰድ ብሎ የለ… በቃ በነጋታው ስናይፐር የያዘ ወታደር አሰማርቶ ለተቃውሞ የወጣውን ሁላ ጠብ ጠብ… ማድረግ ነው።
ህዝብ ደም ካየ ይሸሻል። ጸጥ ይላል። ግፋ ቢል አንድ አራት መቶ አምስት መቶ ሰው ቢገድሉ… በቃ… የተቀረው ህዝብ ዝም ይላል… ከሁሉ ከሁሉ ደሞ ህዝቡ ራስ በራሱ እንዲጠባበቅ የማድረግ ዘዴን መጠቀም አለብዎ… ይሄንንም እኛ ድሮ እና ከናንተ እና ከጥሊያን ነበር የተማርነው እርስዎ ዛሬ እንዴት ይሄ እንደጠፋዎ ገርሞናል።
የምዕራቡ አካባቢ ሰው በሃሳብዎ ያልተስማማ እንደሆነ ለሰሜኑ ህብረተሰብ ‘’የድሮን ስርዓት ሊያመጡብህ ነው…’’ ወይም ደግሞ ‘’ሃገሪቷን ሊበታትኑ አስበው ነው እና ህዝብ ሆይ በንቃት ጠብቅ’’ ብሎ ህዝቡ ራስ በራሱ እንዲጠባበቅ ማድረግ ጥሩ መላ ነው። ለስንቱ ወታደር አቁመው ይዘልቁታል።
የሆነው ሆኖ ግን ግራም ነፈሰ ቀኝ፤ ጠቅላይ ሚኒስትቴርነት ዝም ተብሎ የሚለቀቅ ስልጣን አይደለም። እኛ ሃገር መጥተው ልምድ ቢቀስሙ ሃያ አምስቱንም አመት አንድ መሪ ብቻ ይዘን ያገኙናል። ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባለፈው ሰሞን ‘’ድርጅቴ ከፈቀደ ስልጣን እለቃለሁ’’ ብለው አስደንገጠውን ነበር… (አዩ አይደል እንዲህ ነው የሚባለው….) ይሄው ድርጅታቸው ስላልፈቀደ አሁንም ድረስ ሞተው ሁላ ስልጣን አለቀቁም።
እና ክቡር ዴቪድ ካሜሮን በትንሽ ነገር ተከፍተው ስልጣን ለቃለሁ በማለት ለኛ ህዝብም ክፉ ነገር ባያሳዩብን መልካም ነው… አሁንም ያስቡበት እና ‘’ድርጅቴ አለቅም አለኝ…’’ ብለው ስልጣንዎን ያጥብቁ እኛ ላይም ትችት አያምጡብን.. ለነገሩ እኛጋ ሁሉ ነገር በህግ ነው… በአዲሱ የኮምፒውተር ደህነነት ጥበቃ አዋጅ ስም ማጥፋት የሚያስከስሰውን ክስ ደፍሮ የሚተችን ካለ ይሞክረን።
ከሁሉ ግራ የገባን ቆይ አቃቤ ህጎቻችሁ ፣ ፖሊሶቻችሁ እና ባጠቃላይ የጸረ ሽብር ግብረ ሃይሎቻችሁ ምን ሰርተው ሊበሉ ነው። ከርሶ ሃሳብ ውጪ የሆኑትን አስራ ሰባት ሚሊዮን ሰዎችን ሽብርተኛ ብሎ መፍረድ ያልቻለ ፍርድ ቤትስ ምኑን ፍርድ ቤት ተባለው….

በእውነት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ደግ አልሰሩም! ለማንኛውም ያስቡበት።

Abebe Tolla Feyisa

የጎንደር ሕብረት የተመሰረተበትን ዓላማ እውን ለማድረግ በዋሽንግተን ዲሲ የራት ምሽት አዘጋጀ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በተለይም ከወልቃይት ሕዝብ ጥያቄ ጋር በተያያዘና በሌሎችም ጉዳዮች የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን ሲያደርግ የሰነበተው የጎንደር ሕብረት (ጎሕ) የተመሰረተበትን ዓላማ ዕውን ለማድረግ በዋሽንግተን ዲሲ የራት ምሽት ማዘጋጀቱን አስታውቋል:: በዚህ የራት ምሽት ላይ ፋሲል ደመወዝ; መሀሪ ደገፋው; ሻምበል በላይነህ; ደሳለኝ መልኩና ሌሎችም ድምፃዊያን ሥራቸውን እንደሚያቀርቡ የጎንደር ሕብረት አስታውቆ ዝግጅቱ ጁላይ 30 እንደሚደርግና የመግቢያ ዋጋውም $100 እንደሆነ ገልጿል::

በራሪ ወረቀቱን ለበለጠ መረጃ ያንብቡት

dc flyer2

ፍርድ ቤቱ በእነ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ ብይን ሰጠ

$
0
0

esat

“በኢሳት ሪዲዮና ቴሊቪን ቃለ መጠይቅ ማድረግ፣ የሽብር ድርጊት አለመሆኑ ፍርድ ቤቱ ማረጋገጫ ሰጠ”

ይድነቃቸው ከበደ እንደዘገበው

በእነ መቶ ኣለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ ስር የሚገኙ 16 ተከሳሾች ላይ ብይን ሰጠ። ሰኔ 21 ቀን 2008 ዓ.ም በዋለው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 14ኛ ወንጀል ችሎት በእነመቶ-አለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ ስር በሚገኙ ተከሳሾች ላይ ብይን የተሰጠ ሲሆን ፤ በ5ኛ ተካሽሽ አቶ ዘሪሁን በሬ ፣በ6ኛ ተካሳሽ አቶ ወርቅየ ምስጋናው እና በ7ኛ ተከሳሽ አቶ አማረ መስፍን ላይ የቀረበው ክስ፤ አቃቤ ሕግ በበቂ ሁኔታ በሰው እና በሰነድ ማስረጃ በተከሰሱበት ወንጀል ያስረዳ ባለመሆኑ ሦስቱ ተከሳሾች ፤በተከሰሱበት ክስ መከላከል የማይሰፈልጋቸው በመሆኑ ፍረድ ቤቱ ከተከሰሱበት ክስ ነፃ ናችሁ ብላቸዋል፡፡

በእነ-መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ ሥር የሚገኙት 13ቱ ተከሳሾች ማለትም፡-1ኛ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮነን ፣2ኛ በላይነህ ሲሳይ፣ 3ኛ አለባቸው ማሞ፣ 4ኛ አወቀ ሞኝሆዴ ፣8ኛ ተስፋየ ታሪኩ፣ 9ኛ ቢሆነኝ አለነ ፣10ኛ ተፈሪ ፈንታሁን ፣11ኛ ፈረጀ ሙሉ፣ 12ኛ አትርሳው አስቻለው ፣13ኛ እንግዳው ቃኘው ፣14ኛ አንጋው ተገኘ ፣15ኛ አግባው ሰጠኝ እና16ኛ አባይ ዘውዱ ፣ በተከሰሱበት ክስ እንዲከላከሉ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡

በእነ-መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ የሚገኙት አብዛኛው ተከሳሾች፣ አቃቤ ህግ ያቀረበባቸው ማስረጃ ከኢሳት ሪዲዮ እና ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኞች ማለትም መሳይ መኮንን ፣ፋሲል የኔአለም እና ወንድምአገኝ ጋሹ ጋር በተለያየ ወቅት ቃለ መጠይቅ ማድረጋቸው በማስረጃ ዝርዝር ወስጥ ተካቶ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቱ “በአገሪቷ የበሽብርተኛ ድርጅቶች ዝርዝር ውስጥ ኢሳት አይገኝበትም፡፡ በእርግጥ ኢሳት የተባለው ጣቢያ የሽብር ድርጅት አቋም እና መልዕክት የሚተላለፍበት ቢሆንም፣ ጣቢያው በራሱ የሽብር ድርጅት ነው ማለት የሚያስችል ምን አይነት የህግ አግባብ የለውም በማለት ፍርድ ቤቱ ከኢሳት ጋር ተያይዞ የቀረበውን ማስረጃ ውድቅ አድርጎታል፡፡

ይሁን እንጂ 15ኛ ተከሳሽ አቶ አግባው ሰጠኝ “ቀኑ በትክክል ተለይቶ ባልታወቀ በጥር እና በየካቲት ወር 2006 ዓ.ም ከኢሳት ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ጋር የኢትዮጵያ መንግሥት በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉትን፣ እያሰረና እያሰቃየ በመሆኑ በሰላማዊ መንገድ መታገል አይቻልም” በማለት ቃለ መጠይቅ በማድረጉ በቀረበበት ክስ እንዲከላከል ፍርድ ቤቱ የወሰነበት ሲሆን፤ ለብይኑ መነሻ ያደረገውም “በሰላማዊ መንገድ መታገል አይቻልም” የሚለው አረፍተ ነገር “በሕገመንግስቱ የተደነገገውን በሰላማዊ መንገድ የመደራጀትና ሃሳብን የመግለፅ መብትን የሚፃረር ነው” በማለት ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ በ13ቱ ተከሳሾች ላይ የመከላኪያ መስክር ለመስማት ለነሐሴ 18፣19 እና 20 ቀጠሮ ይዟል፡፡

አትኩሮት ያላገኘዉ በኦጋዴን በሚገኙ በሙስሊም ኢትዮጵያዉያን ላይ እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጽዳት ወንጀል (ሊደመጥ የሚገባው የሳዲቅ አህመድ ትንታኔ)

$
0
0

ላለፉት ሀያ አራት አመታት በኦጋዴን ዉስጥ የሚገኙ ሙስሊም ኢትዮጵያዉያን በህወሃት የሚመራዉ መንግስት የጅምላ ግድያ፣ የጅምላ እስር፣የአስገድዶ መድፈር ሰለባ መሆናቸዉ እምብዛም አለም አቀፋዊ ትኩረት ያላገኘ የዘር ማጽዳት ወንጀል እንደሆነ ይታወቃል።


አትኩሮት ያላገኘዉ በኦጋዴን በሚገኙ በሙስሊም ኢትዮጵያዉያን ላይ እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጽዳት ወንጀል (ሊደመጥ የሚገባው የሳዲቅ አህመድ ትንታኔ)

አተት በአዲስ አበባ በመዛመት ላይ ነው –የሞቱ ሰዎች አሉ

$
0
0

(ዜና ሐተታ)
(ኢትዮ-ምኅዳር ጋዜጣ ቅጽ 04፣ ቁጥር 137)

በአዲስ አበባ ከተማ ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ በርካታ ሰዎች በአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) ሳቢያ ለጤና መታወክ መዳረጋቸውንና የሞቱ ሰዎችም እንዳሉ ከየክፍለ ከተማው የጤና ተቋማት ያሰባሰብነው መረጃ ያመላክታል፡፡

File Photo

File Photo

ንፋስ ስልክ ላፍቶ እና ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተሞች በብዛት ችግሩ የታየባቸው ሲሆን፣ ወረርሽኙ በየካ እና በቦሌ ክፍለ ከተሞችም ተዛምቶ ቀጥሏል ብለዋል፡፡
በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ጤና ጣቢያ ባለፈው እሁድ ለሊት በአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) ሳቢያ ሕይወቱ ያለፈ የቦሌ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የ40 ዓመት ጎልማሳ ሰው እንደነበር የዓይን እማኞች ለዘጋቢያችን ገልጸዋል፡፡

አስከሬኑም ከጤና ጣቢያው ሲወጣ የተባበሩት መንግሥታት ሰዎች መኖራቸውን የዓይን እማኞች ለኢትዮ-ምኅዳር ገልጸዋል፤ በሌሎች ጣቢያዎችም ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ የሞተ ሰው መኖሩን ጠቁመዋል፡፡

የቦሌ ክፍለ ከተማ በ‹‹አሞራው›› (ተንቀሳቃሽ) ጤና ጣቢያ፣ የየካ ክፍለ ከተማ ደግሞ ቀደም ሲል ለኢቦላ ማዕከል ሆኖ አገልግሎት ይሰጥ የነበረው የአባዶ ጤና ጣቢያ የሕክምና ማዕከል የህሙማን የለይቶ ሕክምና አገልግሎት እየተሰጣቸው እንደሆነ ለማወቅ ችለናል፡፡
የበሽታው መዛመቻ ምንጭ የተበከለ ውኃ፣ የተበከለ ምግብና የመጸዳጃ ቤት አጠቃቀም ችግር፣ እንዲሁም የግልና የአካባቢ ንጽህና አለመጠበቅ ሊሆን እንደሚችል ኢትዮ-ምኅዳር ያናገራቸው የሕክምና ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡

አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) በአጭር ጊዜ ውስጥ በድንገት የሚጀምር ትኩሳትና የሆድ ቁርጠት ምልክት የሌለው ተቅማጥ ሲሆን፣ በበሽታው የተጠቃው ሰው ከፍተኛ የሆነ ማስመለስ ይኖረዋል፤ የሰውነት ፈሳሽ መድረቅ ይገጥመዋል፡፡

ይህ የበሽታ ምልክት የታየበት ሰው በፍጥነት ወደ ጤና ተቋም ካልደረሰ፣ በሰውነት ፈሳሽ መድረቅና ማለቅ ምክንያት፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ታማሚው ለህልፈት ሊዳረግ እንደሚችልም የሕክምና ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡

የኢትዮጵያ ውኃና ፍሳሽ መሥሪያ ቤት የሚጠቀምባቸውቸው ቀደምት የውኃ ማስተላለፊያዎችና የቦኖ ብረቶች በዓለማቀፍ ደረጃ ጊዜ ያለፈባቸውና ለውኃ ብክለት የሚያጋልጡ እንደሆኑ በተደጋጋሚ የተገለጠ ጉዳይ ነው፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱት የጎርፍ አደጋዎች የመጠጥ ውኃ ብክለትን ሊያስነሱና ለአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) ሊያጋልጡ ይችላሉ ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ እንደገለጸው ደግሞ፣ በዚህ ሳምንት 300 ሰዎች በአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) ታመው ለህክምና አገልግሎት በተለያዩ ጤና ጣቢያዎች መወሰዳቸውን ገልፆ፤ ሆኖም እስከ አሁን አንድም ሰው በበሽታው አልሞተም ብሏል፡፡

የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ፣ በአዲስ አበባ በሁሉም ክፍለ ከተሞች በአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) ቢያንስ አንድና ሁለት ሰው በበሽታው ተጠቅተው በህክምና አገልግሎት ላይ መሆናቸውን ገልፆ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ለዚህ ለለይቶ ህክምና አገልግሎት 25 ጣቢያዎች ተቋቁመው በማገልገል ላይ ናቸው ብሏል፡፡
መንግሥት በበኩሉ፣ በሽታው በተበከሉ ምግቦች፣ የመጠጥ ውኃና በሌሎች መተላለፊያ መንገዶች በቀላሉ ከሰው ወደ ሰው መተላለፍ የሚችል ስለሆነ፣ ዜጎች ለግልና ለአካባቢ ንጽህና የተለየ ትኩረት መስጠት አለባቸው በማለት በትምህርት ቤትና በተለያዩ ተቋማት የማንቃት ሥራ እያከናወነ መሆኑን ገልጿል።

ውኃን አፍልቶና አቀዝቅዞ በመጠቀም፣ ምግብን አብስሎ በትኩስነቱ በመመገብ፣ የምግብ ዕቃዎችና መፀዳጃ ቤትን ንፅህና በመጠበቅ፣ ከቤት የሚወጡ ቆሻሻዎች ውኃን እንዳይበክሉ በማድረግ በሽታውን በቀላሉ መከላከል ይቻላል ብሏል።

የበሽታው ምልክት ሲታይም ለዚሁ ወደ ተዘጋጁ የለይቶ ሕክምና ማዕከላትና የጤና ተቋማት ቀርቦ ህክምና መውሰድ የግድ አስፈላጊ ነው ሲል አስታውቋል።
አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በዚህ ዓመት በሞያሌ እና በአርባ ምንጭ ተከስቶ እንደነበር አይዘነጋም፡፡
(ኢትዮ-ምኅዳር ጋዜጣ ቅጽ 04፣ ቁጥር 137)

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች ሰቆቃ፤ –በበ. ደ. ኮሬ፡ ቶሮንቶ፤ ካናዳ

$
0
0

 

Ethiopian-Airlines-Logo

እነሆ ከሁለት ወራት በፊት ቶሮንቶ ስገባ፤ በረጅሙ ነበር እፎይ ….. ብዬ የተነፈስኩት፡፡ ለረጅም ዘመን በሰቀንና በፍርሀት ውስት ስለኖርኩ፤ አሁንም ሙሉ በሙሉ ነጻነት ተስምቶኛል ብዬ ባላስብም፤ ለጊዜው ግን የተሰማኝ እፎይታ ነው፡፡ መንግስታችን በሚከተለው “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል” አስተሳሰብ የፈጠረውን ድህነትና የትምህርት ዋጋ ማጣትን እንደ ልማት ከተጠቀሙ ድርጅቶች አንዱና ተቀዳሚው የራሱን ዜጎች ማክበር አቅቶት ስለ አህጉር የሚያወራው አየር መንገዳችን፤ ስርዐቱን ጠብቆ ባልተጠና መልኩ የሚከተለው የሰው ሀይል አስተዳደር ቢሮው፤ በየጊዜው የተማረውን እና ሀገር ተረካቢውን የሰው ሀይል እንደ ቤተ ሙከራ ግብዐት እየተጠቀመ፤ ዜጎችን በዕዳ ተብትቦ ዘመናዊ ባርነትን ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡

 

ከእያንዳንዱ ስኬት በስተጀርባ የጠንካራ ሰራተኞች የሌት ተቀን ልፋት መነሳቱ አይቀሬ ነውና፤ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ተልዕኮ መሳካት ከሚሳተፉት ውስጥ የጥገና ባለሞያዎች ሚና በከፍተኛ የሚጠቀስ ነው፡፡ ታዲያ በዚህ ክፍል ውስጥ የተለያየ ማንነትና ትምህርት ደረጃ ያላቸው ሰራተኞች የያዘው አየር መንገዳችን፤ ከፍተኛ ጥንቃቄ በሚጠይቀው የአቬሽን ሙያ ላይ ያሰማራቸው ዜጎቹን ለተከታታይ ስምንት የስራ ሰዐታት ዳቦና ሻይ እያበላ፤ አቅማቸውና የስራ ደረጃቸው ከሚፈቅደው በላይ ሰራ በማሰራት በጫና ምክንያት ለሚፈጠሩ ስህተቶች፤ የሀገር ንብረት ሆነ ብላችሁ ለማጥፋት ወይም የተቃዋሚ ፓርቲ አባል ናችሁ በሚል ሰበብ፤ ማዕከላዊ አስገብቶ ከማስደብደብ፤ እስከ ቤተሰብ በታኙ እስር ማድረስ የተለመደ ተግባሩ እየሆነ መጥቷል፡፡ የስራ ቋንቋውን ወደትግርኛ የቀየረው የድርጅቱ ጥበቃ ክፍል ዋነኛ ግቡ ሰራተኛውን ማንገላታት ካደረገው ሰንበት ብሏል፣ ሰራተኛው ተስፋ ቆርጦ መባረሩን ወይም መታሰሩን እየጠበቀ ይገኛል፡፡ ግቢው ውስጥ ፈገግታ የሚታየው ከላይ ያሉ ሰዎች ፎቶግራፍ ሲለጥፉ ብቻ እየሆነ መጥቷል፡፡

 

ለምሳሌ፤የLine maintenance ስራ፤ ከጠዋቱ 6 am – 2 pm ድረስ ይቆያል፡፡ ከላይ እንደጠየቅኩት፤ ይህን ያህል ሰዓት፤ ያለምንም ምግብ አቅርቦት (ሻይና ዳቦ) እንዲሁም በቂ እረፈት ይከናወናል፡፡ በእነዚህ ጉዳዮች ላይም ይሁን በሌሎች ተጓዳኝ ጉዳዮች ላይ ጥያቄ በሚያነሳ ሰራተኛ ላይ ማስፈራሪያና ሌላም እርምጃ ይወሰዳል፡፡ ለምሳሌ ያህል ከ promotion & training ማስተጓጎል፣ ተገቢውን ጥቅም መከልከል፣ ከ Europe & North America flight ላይ ማገድ በተጨማሪም የ security ክትትል እንዲደረግባቸው ማድረግ ናቸው፡፡ አሁን አሁን ምርጫ ጠፍቶ እንጂ፤ አስተዳደሩ፤ የሰሜን አሜሪካና የአውሮፓ በራሪዎች ያንድ ብሄር ብቻ ተወላጆች ቢሆኑ ይወዱ ነበር፡፡

 

ከ January 1, 2016 ጀምሮ የሚተገበር የ maintenance ሰራተኞችን የዕድገት ደሞዝ እርከን ሰራተኛውን ሳያማክሩ መቀነስ እና ስብሰባ ጠርተው በዚህ ዙርያ ጥያቄ ለሚያነሳ ወገን ማስፈራሪያ መስጠት የተለመደ ነው፡፡ ለምሳሌ ካልፈለጋችሁ እናንት ጥላችሁ መሄድ ትችላላችሁ፤ እኛ ደግሞ ያስተማርንበትን እናስተፋችኋለን በማለት በሀላፊው አቶ መስፍን ማስፈራሪያና እና ንቀት ያዘለ መልዕክት መተላለፉ የዘወትር ቀለብ ነው፡፡

 

ሰራተኛውን ያለፍላጎቱ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ላይ ማሳተፍ ሌላው በደል ነው፡፡ ለምሳሌ የግንበት 20 በአል ማክበር እና የመለስ ሙት አመትን በግድ ሻማ እንዲያበሩ ሰራተኞችን ማስገደድ ጉልህ ምሳሌ ነው፡፡ ያለ ሰራተኛው ፍቃድ (ሰራተኛውን ሳያማክሩ) ከደሞዝ ላይ የተለያዩ መዎጮ መቁረጥ፣ ያለ ሰራተኛው ፈቃድ ወይም ተጨማሪ ክፍያ ስምምነቱ ከሚፈቅደው በላይ ማሰራት እና ጥያቄ የሚጠየቁ ሰራተኞችን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መቅጣት የተለመደ ነው፡፡

 

ብሄርን መሰረት ያደረገ ውይይትም ትችትም አልወድም፡፡ ነገር ግን ይሄ ስርአት ያመጣብን አንድ ነገር ቢኖር፤ ብሄርን መሰረት ያደረገ ውይይትና ትችት ውስጥ እንድንገባ ማድረጉ ነው፡፡ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ግቢና በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ ያሉትን ቁልፍ ቦታዎች ለትግራይ ተወላጆች መስጠት ህግ እየሆነ መጥቷል ማለት ይቻላል፡፡ ቁልፍ ቦታዎችን ይዘው ቢተዉንም መልካም ነበር፡፡ ከዚም አልፈው መቆሚያ መቀመጫ ያሳጡናል እንጂ፡፡ የትግራይ ብሔር ተወላጅና የሕወሀት ደጋፊዎች በ እነ Yibrah Welderufael (የጂኔራሉ ልጅ) ፣ Kibrom (wide body hangar acting manager) እና በአቶ ዘላለም (base maintenance director) የተደራጀው ቡድን በግቢው ውስጥ የሚገኙ የትግራይ ክልል ተወላጆችን ባጣመረ መልኩ ሰራተኛውን የመሰለልና ከፍተኛ ጫና ፈጥሮ የማሰልቸት ዕቅድ ይዘው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡

 

በዚህ ረገድ እንደምሳሌዎች መጠቀስ ያለባቸው፤ የትግራይ ክልል ተወላጅ የሆነ ሰራተኛ ምንም አይነት ጥፋት ቢሰራ የመከላከል እና በእሱ ላይ ህጉን አክብረው የሚያስዳድሩትን አለቆች ግን ምክንያት ፈጥሮ እስከማባረር መድረሱን ነው፡፡ በግቢው ውስጥ የማን አለብኝነት እና የባለቤትነት ስሜት ማስረፅም አንዱ ጉልህ መጠቀስ ያለበት ምሳሌ ነው፡፡ ሶሻል ሚድያ ላይ ከሕወሀት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር የተነሱአቸውን ፎቶግራፎች (Photographs) በተደጋጋሚ መልቀቅና አንድ አንድ ፖለቲካዊ መልእክቶችን ማስቀመጥ የመወደጃ መስፈርት ነው፡፡ ለመብታቸው ጥያቄ የሚያቀርቡ ሰራተኞችን ያለ ምክንያት የማንገላታትና ከSecurity ጋር ግንኙነት እንዳላቸው አስመስለው ከስራ እስከ ማሰናበትም ሌላኛው ክፉ ድርጊት ነው፡፡

 

ከግቢው የ security ቡድን ጋር እጅና ጓንት ሆነው በመሰራት ያሻቸውን ምክንያት እየፈለጉና እያስፈለጉ ሰራተኛውን ማንገላታት፤ በዝምድና እና በእውቅና መሿሿም እንዲሁም ለአለቆች የማጎብደድን ስርዓት ፈጥረው በሰራተኛው ዘንድ ጫና ማሳደር የተለመዱ ናቸው፡፡ ለምሳሌ፡ በአሁኑ ሰዐት Lome በሚገኘው hub director ሆኖ የተሾመው እና የቀድሞው የ line maintenance director አቶ ቅዱስ መልካሙ የ CEO (ተወልደ ገ/ማርያም) የባለቤቱ እህት ልጅ መሆኑ ይታወቃል፡፡

 

የሴኩሪቲ አባላት ላይ ያለውን ወሳኙን እና የአመራሩን ቦታ በትግራይ ተወላጆች መሙላት፣ ከዚህ በፊት ቃሊቲ ወህኔ ቤት ይሰራ በነበረው በቅፅል ሰሙ “ወዲ ሻምበል” በሚባለው ግለሰብ የሚመራው የድርጅቱ ሴኩሪቲ ለፖለቲካው ጥቅም ሲባል ሰራተኛው ለይ በተለያ መልኩ ጥቃት እያደረሱ ይገኛሉ፡፡ አንዳንድ ግዜ ሰራተኛውን የሚያንገላቱበት ሰበብ ተራና የወረደ ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል የድርጅቱን ንብረት በማን አለብኝነት የሚጠቀሙት እኚሁ የሴኩሪቲ አባላት፤ ሌላውን ሰራተኛ የታሸገ ውሀ ለምን ጠጣህ፤ ኩኪስ በላህ፤ ብለው መታወቂያ ቀምቶ በሰዎች ፊት ከማንገላታትና ከማዋረድ፤ እስከ ደሞዝ ቅጣት ያደርሳሉ፡፡ ያም አልበቃ ካላቸው አለባበስህ አያምርም ወይም ፂምህን ለምን እንዲህ ተቆረጥክ በማለት ከስራ ቦታ እስከማስወጣት ደርሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየርመንገድ ሰራተኞች የሚኖሩበት ግፍ አያሌ ነው፡፡

 

ነፃ አውጭዎቻችን እንደ ኮንስትራክሽን ዘርፉ ዜግነትን በደረጃ ወረቀት ላይ ባያስቀምጡትም፤ መተግበሩ ላይ ግን ከራሳቸው አልፈው ለልጆቻቸው እያወረሱ መሆኑን የሚያሳዩ ምልክቶች በየቢሮዎችና በከተማ ውስጥ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች መገንዘብ ከበድ ያለ አይመስልም፡፡ የዚሁ ደረጃ ተጠቃሚዎች በዚህ ድርጅት ውስጥ መንፀባረቅ ከጀመረ ጥቂት ጊዚያት ተቆጥረዋል፡፡ ለምሳሌ ያህል የአንድ መከለከያ ባለስልጣን ልጅ በአጭር ጊዜ የስራ ልምድ ግቢው ውስጥ ያሻውን እያደረገ ነው፡፡ በዘር ላይ ያተኮረ ቡድን ተሰማርቶ የሰራተኛውን ህልውና የሚነኩ ተግባራትን መፈፀም እስከ ማባረር ባለመብት መሆን፤ መቼም ልጆቻችሁ ይህን ጉዳይ በዚህ መልኩ ከያዙላችሁ እናንተ ደግሞ ብዙ ሚሊዮን ህዝብ በተራበበት ሀገር ባመቻቻችሁት የግብር ስርዐት ባጠራቀማችሁት ገንዘብ በትንሿ ልጃችሁ ስም ባደጉ ሀገራት ቤትና መኪና ገዝታችሁ ኑሮአችሁን እንዳመቻቻችሁ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡

 

ለዛሬ እዚህ ላይ ብቃኝ፡፡ ወደፊት ደግሞ በኔ ላይ የደረሰውን ጨምሬ ከሌላ ጽሁፍ ጋር እንገናኛለን፡፡

 

በበ. ደ. ኮሬ፡ ቶሮንቶ፤ ካናዳ፤ ሰኔ፤ 2008/2016

 

 

 

 


አበራ ነጋሣ -ከአንዱዓለም ተፈራ

$
0
0
comment symbol icon

comment symbol icon

የልጁን ፊት አተኩሮ እየተመለከተ፤ በልቡ በጣም ሩቅ ወደሆነ የማያውቀው ሀገር ዘመተ። ልጁ የአስራ ስድስት ዓመት ወጣት ነው። አባቱን አስታውሶ ነጋሳ ብሎ ስይሞታል። እናም የልጁ ስም ነጋሳ አበራ፤ የሱ ስም አበራ ነጋሳ ነው። አበራ ነጋሳ የተወለደው አዘዞ ከተማ ነበር። አዘዞ፤ ከጎንደር ከተማ ወደ አየር ማረፊያው ሲሄዱ፤ ከከተማው አስራ ሁለት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ፤ አየር ማረፍያው ከመድረሱ በፊት ደግሞ፤ ሶስት ኪሎ ሜትር ቀድማ ትገኛለች። አዘዞ የወታደር ሰፈር ነበረች። ባለፈው የ፳ኛው ምዕተ ዓመት አጋማሽ አካባቢ፤ የሰሜኑን ሀገራችንን ለመከላከል የተቋቋመው የ፪ኛ ክፍል ጦር፤ ከሶስቱ ብርጌዶች አንዱ፤ የ፰ ብርጌድ፤ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ያለውን ደንበር ለመጠበቅ አዘዞ ሰፍሮ ነበር። ይህ የ፰ ብርጌድ፤ ሶስት የሻለቃ ጦሮችና አባሪ የከባድ መሳሪያ፤ የሕክምና፣ የመገናኛና የዋናው መስሪያ ቤት ከፍል ሲኖሩት፤ አንዱ ፩ኛ ሻለቃ ጦር ጎርጎራ፤ ሁለቱ ደግሞ፤ ከአባሪ ክፍሎቹ ጋር አዘዞና አየር ማረፊያው ነበሩ። እኒህ የሻለቃ ጦሮች ፍጹም ተደላድለው የተቀመጡ አልነበሩም። ከአካባቢው ተወላጆች በተመለመሉ ወታደሮች የተሞላው የጎርጎራው የሻለቃ ጦር፤ በ፲ ፱ ፻ ፶ ፮ ዓመተ ምህረት ገደማ፤ በሶማሊያ የተቃጣውን አደጋ አስመልክቶ፤ የሶስተኛውን ክፍለ ጦር ሊረዳ ወደ ኦጋዴን ሄዶ፤ በዚያው ተመድቦ ቀርቷል። አዘዞ የነበረውም የ፬ኛው ሻለቃ ጦር ከኮንጎ ከተመለሰ በኋላ ኤርትራ ተልኮ፤ የምዕራባዊ ቆላውን፤ አቆርደትን፣ ከረንንና ተሰነይን ከ፲ ፱ ፻ ፶ ፯ ዓመተ ምህረት ጀምሮ ቤቱ አድርጓል። በዚያ ምትክ ደግሞ፤ አየር ማረፊያው ላይ አዲስ ሁለት የ፳ ፬ኛና የ፴ ፩ኛ የሻለቃ ጦሮች ተመስርተው ነበር።

የአበራ ነጋሳ አባት ወደ አዘዞ የመጡት፤ ከ፲ ፱ ፻ ፶ ፫ቱ መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በኋላ ነበር። ወታደር ነጋሳ ኦላና፤ በጣም ረጅምና ቀጥ ያሉ፤ በወቅቱ አዲስ አበባ በክብር ዘበኛነት ተመልምለው ያገለግሉ የነበሩ የጦር ሠራዊቱ አባል ነበሩ። በመፈንቅለ መንግሥቱ ጊዜ ምን እንደተደረገ ፍጹም አያውቁም። ብቻ አብረው ከምድብ ወታደሮቻቸው ጋር ባንድ ጎራ ሆነው ተኩስ እንደተጀመረ ያስታውሳሉ። ሆኖም የመፈንቅለ መንግሥቱ ሙከራ ከከሸፈ በኋላ፤ ተሸናፊ ሆነው መማረካቸውን ያውቃሉ። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ከብዙ ወታደሮች ጋር አዘዞ ካለው የ፰ኛ ብርጌድ ተመድበው ተቀላቅለዋል። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ከዚህ ዓለም እስከ ተለዩ ድረስ፤ አዘዞን ቤታቸው አድርገዋል። በመጡ በሶስተኛው ዓመት፤ የጠገዴ ተወላጅ የሆኑትን ወይዘሮ አልጠገብን አግብተው ሙሽሪትን፣ ፋሲካንና አበራን ወልደዋል። አበራ የተወለደው መስከረም ፲ ፮ ቀን ፲ ፱ ፻ ፷ ፩ ዓመተ ምህርት ነው። አባቱ አበራን ሰላሌ ስለሚገኙት ዘመዶቻቸው ብዙ አስተምረዉታል። ዘመዶቹን አንድ ቀን ሄዶ እንዲገናኝ ሲያስቡ፤ ሳይሳካላቸው ቀርቷል። የወታደር ደሞዝና የመጓጓዣው ወጪ አልጣጣም ብሏቸው፤ ዛሬ ነገ ሲሉ በርጅና ዘመናቸው ድንገት ታመው ተለዩት። የቀብር ስነ ሥርዓታቸው የተፈጸመው ሎዛ ማርያም ቤተ ክርስትያን ነው። ከአዘዞ ሰው ሌላ የሚዛመዱት ሰው አልተገኘም። እናቱም ወይዘሮ አትጠገብ፤ አዘዞ ተክለሃይማኖት ነው የተቀበሩት።

ወታደር ነጋሳ ልጃቸውን አበራን በደንብ አስተምረው፤ በሀገራቸው ታላቅ ሰው እንዲሆንላቸው ጥረዋል። ሴቶቹን ብዙም ለትምህርታቸው አልተጨነቁም ነበርና ለወታደሮች ዳሯቸው። አበራም አዘዞ ሲያድግ፤ ከአፄ ፋሲል ትምህርት ቤት ጓደኞቹ ከነአበራ ደለሳ፣ ተረፈ ነጋሳ፣ አበራ ወልደየስ፣ ቢራራ ተስፋሚካዔል፣ ይሁኔ ጌታሁን፣ ሙሉዬ መኮንን፡ ሰለሞን ሻንካ ጋር ሆኖ፤ የሎዛ ማርያም አስተሮዬ ሲከበር፤ የኦሮሞኛ፣ የወላይትኛ፣ የትግርኛ፣ የአማርኛ፣ የጉራግኛ፣ የአፋርኛ፣ የሶማልኛ ዘፈኖችን ይጨፍር ነበር። አበራ እንዳባቱ ሎጋና ቀጥ ያለ ወታደራዊ አቋቋም ስለነበረው፤ ጓደኞቹ ሽምበቆው የሚል ስም ሠጥተውታል። ጓደኛሞች የሆኑ ያዘዞ ልጆች፤ ስም መሠጣጠት ያውቁበታል። ቁራ፣ ድምቢጥ፣ ድንች፣ ሱዘንድ፣ ዋንዛ፣ ድኩሌ፣ ቡሊት፣ ሰማይ ዳሱ፣ ኳስ ፊደሉ፣ ቁንን ከስሞቹ ጥቂቶቹ ነበሩ። በአስተሮዬ የጥምቀት ዘፈን ጊዜ፤ ምንም እንኳ ዜማ አውጪዎቹና ትክክለኛ ጨፋሪዎቹ ቁጥራቸው አነስተኛ ቢሆኑም፤ አብረው የሚጨፍሩት ወጣቶችና ሌሎች ወታደሮች በሙሉ፤ የዘፈኑ የጋራ ባለቤት ነበሩ። በየዓመቱ የማይለዩት ገብሬ ሽበሺ ከጎንደር እና አለቃ አድማሱ ከአዘዞ፤ ገብሬ ሽበሽ እማማ ውብ ናት ደማም ናትን ሲያወርድ፤ አለቃ አድማሱ በዘነዘና ቁመናቸው እስክስታውን ሲያወርዱት ለጉድ ነበር።

አዘዞ የሁሉም ቤት ነበረች። ዘፈኑ ሁሉ የኢትዮጵያ ዘፈን፣ ቋንቋው ሁሉ የኢትዮጵያ ቋንቋ ይባሉ ነበር። የትኛውም የኢትዮጵያ ክፍል ለመጣ ኢትዮጵያዊ፤ አዘዞ ቤቱ ነበረች። አዘዞ አንድ ዓመት አፄ ፋሲል ትምህርት ቤት የተማረ ወጣት፤ የአዘዞ ልጅ ተብሎ ይታወቃል። ወታደሮች፤ ሁሉም ከወታደሩ ሰፈር (ካምቦ) የድማዛ ድልድይን ተሻግረው፤ የሲቪሉ ሰፈር (ብላጆ) ቤት ገዝተው፤ የጡሮታ ጊዜያቸውን ያሳልፉ ነበር። ከአስመራ የመጡት አዘዞ ያገኙዋቸውን አግብተው ወልደው ከብደው አዘዞን ቤታቸው አድርገዋል። ከሐረር ጀምሮ እስከ ወለጋ፤ ከሲዳማ እስከ ትግራይ የመጡትም እንዲሁ። ከአዘዞ ተቀይረው የሄዱም በዚያው አግብተው ከትመዋል። አንዳንዶቹ ተመልሰው አዘዞ በመመደብ ቤተሰባቸውን ይዘው መጥተዋል። መጋባቱ፣ ክርስትና መነሳሳቱ፣ ማኅበሩና እድሩ፣ ቁቡና ስንበቴው ድብልቅልቅ ያለ ነበር።

ያች የአስተሮዬ ቀን፤ በወታደሮችና በአዘዞ ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን፤ በድፍን ጎንደርና በአካባቢው ባሉ ትንንሽ ከተሞች በናፍቆት የምትጠበቅ ነበረች። ላብ በላብ እስኪሆኑ የሚጨፍሩት እድምተኞች፤ መብላት ረስተው ተጎትተው እስኪወሰዱ ድረስ መድረኩን አይለቁም ነበር። በአዘዞ የአስተሮዬን በዓል ለማክበር የሚታረደው ዳንግሌ በግ፣ ዳጉሳ አውራ ደሮ፣ የሚጎዘጎዘው ግጫ ሣርና የሚጤሰው ጠጅ ሳር ለጉድ ነበር። ብሉልኝ ጠጡልኝ እየተባሉ በየመንገዱ የሚጎተቱት እንግዶች ብዙዎች ነበሩ። በአስተሮዬ አዘዞ የድግስ ከተማ ነበረች። አዘዞ በአፄ ቴዎድሮስ ጊዜ የጦራቸው ማሳረፊያ እንደነበረች ይነገራል። ቀድሞ በተክለሃይማኖት ደብሩ ዙሪያ ያለው የመጀመሪያው የነዋሪዎች መንደር፤ ደብረዘይት ተብሎ ይታወቅ እንደነበር ተክለሃይማኖት ያለው መጽሐፍ ያትታል።

ከወታደር ሰፈሩ አልፎ የድማዛን ድልድይ ተሻግሮ ያለው ነዋሪ፤ እንደ የጦር ሰፈሩ ሁሉ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ ነበሩ። እንዲያውም በሚያስገርም ሁኔታ ከውጪ ሀገር የመጡ ሁሉ ቤታቸው ያደረጉበት ሰፈር ነበር። ከሁለቱ የሰሜንና የደቡብ የመኖች የመጡ ነጋዴዎች፤ ኢትዮጵያዊያን ሚስቶችን ከዚሁ አግብተው፤ ሱቆችን በሙሉ ይዘው ነበር። ሀጅ አሊ፤ አሊ ዞማ፣ መረጡ፣ መሐመድ አሊ፣ አሊ በርሚል፣ ጥቂቶቹ ነበሩ። ሰፈሩ መስጊድ ሲኖረው፤ ቤተ ክርስትያን ግን አልነበረበትም። የሎዛና የተክለሃይማኖት ደብሮች ያሉት በወታደሩ ሰፈር ወገን ነው። የሲቪሉ ሰፈር፤ እንደ ወታደሩ ሰፈር በጣሊያን ፋሽስቱ አጭር ጊዜ ወረራ የተሰሩ ቤቶች ብዙ ባይኖሩትም፤ ከድማዛ ጥግ የነበረው አስተዳዳሪው የነበሩበት ቤትና መሐል ገበያው ላይ ያለው ወፍጮ የተተከለበት ቤት፤ የፋሽስቱ ጣሊያ ቅሪት ነበሩ። የብርጌዱ መኪና ጠጋኝ አብደል ራህማን እድሪስ፣ ጠንቋዮች እነ የማነ ብርሃን፣ አለቃ አድማሱ፣ የከተማው አድማቂዎች ነበሩ። ግርማይ “ደንጊያ ወርዋሪው”፣ ዋንዛዬ “ጠጠው በል!” ማማ አዋጉ እብዲቱ፤ ከማል ዱክየው፡ አበባው ዘላኔ እብዱ፣ የከተማዋ ትክሎች ነበሩ። አባ መልኬም የሠራዊቱ ቄስ ነበሩ። ቀደም ብሎ ጁዳ የሚባል ሕንድ፤ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ሆኖ እዚያው ትምህርት ቤቱ ውስጥ ከባለቤቱና ከልጆቹ ጋር ይኖር ነበር።

አበራ ነጋሣ አዘዞ አፄ ፋሲል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ትምህርቱን አጠናቆ፤ ወደ ጎንደር የቀዳማዊ ኋይለ ስላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሄደ። የአስረኛ ክፍል ተማሪ በነበረበት ወቅት፤ ለመምህርነት ሙያ ሥልጠና ፈተና አልፎ፤ ወደ ሐረር ተጓዘ። ሐረር በትምህርት ላይ ሳለ፤ አዘዞ አብራው ከተማረችውና ወደዚሁ አብራው ከመጣችው ከፀሐይ ተስፋእግዚ ጋር ጓደኝነቱን አጠበቀ። ፀሐይ ተሰፋእዝጊ የመቶ አለቃ ተስፋእግዚ ልጅ ናት። አባቷ የመቶ አለቃ ተስፋእዝጊ ከአስመራ ወደ አዘዞው የ፰ኛ ብርጌድ ተዛውረው የመጡ ነበሩ። የፀሐይ አባትና እናት ወደ አዘዞ ከመምጣታቸው በፊት፤ ከአስመራ ውጪ ፍፁም ተንቀሳቅሰው አያውቁም ነበር። ሁለቱም ወላጆቿ ተወልደው ያደጉት አስመራ ነበር። እናቷ ትምህርት ቤት የመግባትና የመማር ዕድል አልነበራቸውምና፤ አዘዞም መጥተው አማርኛ መናገር ይቸግራቸው ነበር። አባቷ ወታደርነት ተቀጥረው የመቶ አለቅነት እስኪያገኙ ድረስ፤ ያገለገሉት አስመራ በነበረው የ፪ኛ ክፍለ ጦር ውስጥ፤ በአንዱ ብርጌድ፤ በአንዱ የሻለቃ ጦር ተመድበው ነበር። አዲሱን ማዕረግ እንዳገኙ፤ አዘዞ ተመደቡና መጡ። አበራና ፀሐይ የክፍል ጓደኝነታቸው የጀመረው፤ ፀሐይ ከአስመራ እንደመጣች ነበር። ፀሐይ ከክፍል ጓደኞቿ ከነማሚቱ ደለሳ፣ ፀሐይ ጤናው፣ ፀሐይ እቁባይ፣ እናኑ ተገኝ፣ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ነበራት። የአዘዞ ልጆች አብረው ከመማርና አብረው ከትምህርት ቤት ውጪም ጓደኝነት ስለነበራቸው፤ ግንኙነታቸው ዘለቄታ ያለውና አብሮ ከመወለድ ያልተለየ ነበር። ከፊሎቹ ወላጆቻቸው ከሸዋ፣ ከፊሎቹ ደግሞ ከኤርትራ፣ ከሐረር፣ ከትግራይ፣ ከከፋ፣ ከአርሲ፣ ከሲዳማ የመጡ ነበሩ። አዘዞን ትንሿ ኢትዮጵያ ይሏት ነበር ነዋሪዎቿ። አበራና ፀሐይ ሐረር ሲገቡ፤ አብረው ከማደጋቸውና ከወላጆቻቸው በዚህ ርቀት አብረው በመገኘታቸው፤ አዘውትረው ሲገናኙ ወደ ከንፈር ጓደኝነት አመሩ።

አበራና ፀሐይ ከመምህርነት ሥልጠናው ሲመረቁ፤ አብረው እንዲመደቡ ብዙ ጥረት አደረጉ። ለዚህም ይረዳቸው ዘንድ መጋባታቸውን ለትምህርት ቤታቸው አስታወቁ። እናም አብረው አርሲ ውስጥ፤ ከአሰላ ራቅ ባለች ገጠር ቦታ ተመደቡ። ከሶስት ዓመት በኋላ ወደ አዘዞ ተዛወሩ። በዚያን ጊዜ፤ የፀሐይ አባት ጡሮታ ወጥተው፤ ወላጆቿ ወደ አስመራ ተመልሰው ሄደዋል። አዘዞም በሚያውቋቸው ሰዎች መካከል፤ ደግሰው ጋብቻቸውን አሰመሩበት። የአዘዞ ነዋሪዎች ልጆቻቸውን ዳሩ። ፀሐይ አስመራ እየተመላለሰች ወላጆቿን ትጠይቅ ነበር። አበራና ፀሐይ የፖለቲካ ሰው ስላልነበሩ፤ ለ፲ ፱ ፻ ፷ ፮ ቱም ሆነ ለ፲ ፱ ፻ ፹ ፫ቱ የመንግሥት ሥልጣን ቅይይር ምንም ዓይነት ትኩረት አልሠጡትም። “ፖለቲካ የሌሎች ጉዳይ ነው። እኛ መምህራን ነን። የመንግሥት ጉዳ እኛን አያገባንም።” ይሉ ነበር። በ”የዕድገት ኅብረት ዘመቻ” ተብሎ ወጣቶቹ ሲበታተኑም ሆነ በቀይ ሽብር ጭፍጨፋ፤ አልተነኩም። ያ ሁሉ አልፎ አዲስ ገዢ መጥቶ፤ ኤርትራውያን ወደ ሀገራቸው ይመለሱ ተብሎ ሕዝቡ ሁሉ ሲተራመስ፤ ፀሐይ ምንም አልመሰላትም ነበር። ነገር ግን፤ ጉዳዩን በደንብ የተረዱ ጓደኞቿ፤ በቤታቸው ደብቀው አተረፏት። በዚህ ላይ ደግሞ አበራ በባለቤቴ የመጣ የኔ ጉዳይ ነው ብሎ ስለተነሳ፤ የሚችለውን ሁሉ በማድረግ አተረፋት። ፀሀይ ኤርትራዊ ነኝ አላለችም። የድምጽ መስጠቱም ጉዳይ አልነካትም። አሁንም በኢትዮጵያዊነቷ፤ ከኢትዮጵያዊ ባለቤቷና ልጆቿ ጋር ነው የምትኖረው። ፖላቲካን አታምጡብኝ ብላ እንደ ኮረንቲ የምትፈራው ጉዳይ ነው።

አሁን ግን ጊዜው ተለውጧል። አበራና ፀሐይ ችግር ውስጥ ናቸው። ኢትዮጵያ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሀገር መሆኗ ቀርቷል። ኢትዮጵያ የብሔሮችና የብሔረሰቦች ክልሎች ጥርቅም ስለሆነች፤ ግለሰቦች በየብሔሮቻቸው ክልሎች ሲሆኑ ብቻ ነው፤ በክልል አባልነታቸው ኢትዮጵያዊነታቸው የሚታወቀው። ከብሔር ከልሉ የወጣ ግለሰብ፤ እንደውጪ ሀገር ሰው ተባራሪ ነው። እንዲያውም የውጪ ሀገር ግለሰብ የበለጠ ይከበራል። ይህን ደግሞ አስከባሪዎቹ የመንግሥት ካድሬዎች ናቸው። ይህ የገዥዎችን አባሎችና ዘመዶች አይነካም። ለነሱ የተለየ ሕግ አላቸው። ለሕዝቡ የሚያገለግል አንድ ሕግ፤ ለገዥዎቹ የሚያገለግል ደግሞ የተለየ ሕግ፤ በሀገራችን አለ። ያካባቢው ሕዝብ መብት የለውም። መንግሥት የሚለውን መስማትና መንግሥት ያዘዘውን ማድረግ ብቻ ነው ሕዝቡ ያለበት። ምንም እንኳ አብረው ያደጓቸውና የሚያውቃቸው ሁሉ፤ የኛ ናቸው ስለሚል፤ በሕዝቡ በኩል ችግር ባይኖርባቸውም፤ በመንግሥቱ በኩል የሚደርስባቸውን በደል መገመት አይቻልም። አዘዞ ማለት አበራና ፀሐይ፤ አበራና ፀሐይ ማለት አዘዞ ናቸው! ብለው ነው ሁሉም የሚያምኑ። ኤርትራዊያን ይውጡ በተባለበት ጊዜ እንደተደረገው ሁሉ፤ ሕዝቡ እንደሚከላከልላቸው ያውቃሉ። ከመንግሥቱ በኩል ያሉት አዲስ የመጡ ወጣት የኮር አባሎች ግን ሌላ ናቸው። ዛሬ ጊዜ ባለሥልጣኖቹና ወጣቶቹ፤ ቀድሞ ለነበረው የሕዝቡ ግንኙነትና ለቆዬው አስተሳሳሪ ባህል ደንታ የላቸውም። ደንታ የላቸውም ብቻ ሳይሆን፤ አያውቁትም፤ ማወቅም አይፈልጉም። መሪ ድርጅታቸው ከሚነግራቸው ነገር ውጪ፤ ሌላ ትክክል ሆነ ሀቅ የሚባል ሰውም ሆነ ነገር የለም፤ ካለም መኖር ስለሌለበት ይታሰራል፣ ይሰደዳል ወይንም ይገደላል። በፓርቲያቸው የሚነገራቸውን እንደ ቅዱስ ቃል ይዘው ከመብረር በስተቀር፤ ጭንቅላታቸውን ተጠቅመው ሁኔታዎች መመርመርና ውሳኔ መሥጠት ምን እንደሆነ አያውቁም፤ አልሠለጠኒበትም፤ አይፈቀድላቸውም።

በተጨማሪም፤ ሁሉም ለራሱ የሚል መመሪያ ያለ ይመስል፤ እኒህ የገዥው ቡድን አባላት፤ ራሳቸውን ለማበልጸግ፤ መንግሥታዊ መዋቅሩን ለጥጠው ይጠቀሙበታል። ይህ ነው አበራን ያስጨነቀው። “ለምን የልጄን ስም ነጋሳ አልኩት!” ብሎ አሰበ። “እንኳንም አንድ እሱን ብቻ ነጋሳ አልኩት! ሴቶቹን እንኳን የአካባቢውን ስም ሠጠኋቸው!” ብሎ ልቡ በሌሎቹ ላይ ሊደርስ ይችል የነበረውን አስቦ ተረጋጋ። ሴቶቹ ልጆቻቸው፤ ከወታደሮች ባሎቻቸውና ልጆቻቸው ጋር ሆነው፤ ማንነታቸውንም ሆነ የወላጆቻቸውን ማንነት ረስተዋል። ኢትዮጵያዊነታቸውን ብቻ ነው የሚያውቁት። “ሴቶቹን ፀሐዬ የኤርትራ ስም ብትሠጣቸው ኖሮ፤ ምን ይበላን ነበር!” በማለት አሰበ። አባቱ ለኢትዮጵያ ብለው ነበር ወታደር ሆነው ያገለገሉት። እዚህ ሲመደቡም “ሀገሬ ኢትዮጵያ!” ብለው ነበር እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ የኖሩት። “አሁን ሕዝቡ የኔ ነህ እያለኝ፤ እንዴት የመንግሥት ካድሬ ጭንቀት ይፈጥርብኛል!” ብሎ አዘነ። ሕዝቡ ደግሞ ጉልበት የሌለው በሆነበትና መንግሥቱ ያፈተተውን በሚያደግበት ወቅት፤ “ምን ይውጠኝ ይሆን?” የሚለው ልቡን ሰቅዞ ይዞታል። መንግሥቱ የሕዝቡን ድምጽ የሚሰማና ለሕዝቡ የሚያገለግል ሳይሆን፤ ሕዝቡ ለመንግሥቱ አገልጋይና መንግሥቱን ብቻ እንዲሰማ የተገደደ ሆኗል። ጥቂት ያካባቢው ተወላጆች የሆኑ የኮር አባላት ቢኖሩም፤ ለሆዳቸው ያደሩ ስለሆኑ፤ “ደደብ አማራ!” እያሉ ገዥዎቻቸው ሲሰድቧቸው እንኳ፤ ግድ የላቸውም። ሆዳም ማተብ የለውም። ቤቱም ሆዱ ነው።

“የኔስ የኔ ነው። አርጅቻለሁ። ከተወለድኩበት ቀን ይልቅ የመቃብሬ ቀን ይቀርባል። አሳቤ ለልጄ ነው። እኔ የአባቴን የትውልድ ቦታ እንኳን አላውቅ። ያባቴን ቋንቋ አላውቅ። እትብቴ የተቀበረው አዘዞ። ያዘዞ ሰው ደግሞ የኔ ነህ ብሎኛል። አዘዞ የኢትዮጵያ ክፍል ናት። በኢትዮጵያዊነቴ ደግሞ፤ እንኳንስ ተወልጄ የኔ ብዬ ባደግሁበት ቦታ ይቅርና፤ የትም የኢትዮጵያ ክፍል መኖር እችላለሁ። እኔ ደግሞ ያዘዞን የድማዛ ውሃ ጠጥቼ ያደግሁ ያዘዞ ልጅ ነኝ። እንዴት ብዬ ነው ያዘዞ ልጅ አይደለሁም የምለው? ለምን ካዘዞ እባረራለሁ? ተባርሬስ የት ነው የምሄደው? በመንግሥት ፍላጎት የተነሳ እንዲህ ያለ ጣጣ ውስጥ ለምን ገባሁ! አንተ ፈጣሪ ምን በደልኩህ!” በማለት አምላኩን አማረረ። “የሰውን ነገርና ተግባር በአምላክህ አታሳብብ!” የሚለው ከጎኑ ጠፋ።

አበራን ምን ሊውጠው ይሆን? ይህ የአበራ ብቻ ጥያቄ አይደለም። የሁሉም ኢትዮጵያዊ ነኝ ባይ ጥያቄ ነው። ዛሬ ያዲስ አበባ ልጅ ነኝ በማለት እግሩን አፈራግጦ የተቀመጠ ሰው፤ ነገ አዲስ አበባ አልተወለድክም ወይንም ዘርህ አዲስ አበባን አይሸትም፤ የናትህ ዓይንም የተለዬ ነው፤ ተብሎ እንደሚባረር ማወቅ አለበት። መቼ ነው ኢትዮጵያዊነት ማለት በሁሉም መልኩ የኢትዮጵያ ዜጋ መሆንና መብቱም ከዚያ የሚመነጭ የሚሆነው? አበራስ ምን ማድረግ አለበት? ፀሐይስ? ልጆቻቸውስ? በሌሎች ከተሞች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንስ? እስካሁንስ የት ገቡ!

የማለዳ ወግ…”እማ…እንደበቅ “የህጻን ኤማንዳ ሽብር ህይዎት !

$
0
0

የኢትዮጵያ ልጆች –ግጥም

$
0
0
 Tensaye
የኢትዮጵያልጆችድሮምታሪካቸው
ቋንቋቸው ቢለያይ አንድ ህዝብናቸው
አባቱኦሮሞልጅየውአማራ
አጎቱ ጉራጌ አክስቱ ጊሚራ
አያቱ መቀሌ አማቹ ፎገራ
ዘርህን ንገረን ምንድነው ቢሉት
ቋንቋውን ነው አንጂ ዘሩን የት አውቆት
አስቲ ተመልከተው ጎንህ ያለውን ሰው
ከግራም ከቀኝም ከሑዋላም ከፊትም
ምን ይመስላል መልኩ ዘሩን ታውቀዋለህ?
የዘሩን አመጣጥ ግንዱን ትለያለህ?
የሰው ዘር መለያው ቋንቋው ከተባለ
አሜሪካ ሁሉ አንግሊዝበሆነ
እንኳንምአንድአገርተወልደንያደግነው
አንጀራ ወጥ ክትፎ ዳቦየምንገምጠው
ነጭና ጥቁሩም ቢጫውም አንድ ነው
መነሻው ኢትዮጵያ መኖሪያውአለምነው
አመለካከትክን ሰፋብታደርገው
የሰው ዘር በሙሉ ኢትዮጵያዊኮ ነው!!!!
/መስፍን ገናናው

ቤትን ማፍረስና ዜጎችን ማፈናቀል፥የዘር ማጥፋት ወንጀል –ሳዲቅ አህመድ ከዶክተር ግዛቸዉ ተፈራ ቴሶ ጋር

$
0
0

ዶክተር ግዛቸዉ በUrban Planning and Public policy (በከተማ ልማትና የማህበረሰብ ህግ) ዶክተሬታቸዉን ሰርተዋል። በArchitecture ሁለት የማስተርስ ዲግሪዎች፣ በCity and Regional Planning ሌላ ተጨማሪ ድግሪ ያላቸዉ ናቸዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉን የጅምላ ቤት ማፍረስ ሂደት የዘር ማጥፋት ወንጅል ነዉ ሲሉ ይገልጹታል።

ቤትን ማፍረስና ዜጎችን ማፈናቀል፥የዘር ማጥፋት ወንጀል – ሳዲቅ አህመድ ከዶክተር ግዛቸዉ ተፈራ ቴሶ ጋር

የሰይፉ ፋንታሁን የሸገር ቆይታ እስከ መስከረም ተራዘመ (አላሙዲ ለነሰይፉ ባንክ ያስገቡትን ገንዘብ አወጡት)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ሰይፉ ፋንታሁን በሸገር ኤፍ ኤም 102.1 የሚያቀርበውን ‹‹ታዲያስ አዲስ›› የሬዲዮ ፕሮግራም ሰኔ 30 እንዲያቆም ከጣቢያው ደብዳቤ ደርሶት ነበር፡፡ ይሁንና እንደምንጮችችን ገለፃ ይህ ውሳኔ ተቀልብሶ እስከ መስከረም ፕሮግራሙን እያቀረበ እንዲቀጥል ተራዝሞለታል፡፡ በአሁኑ ወቅት ለቤተሰብ ጉዳይ በአሜሪካ የምትገኘው የሸገር ሀላፊ አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ የሰይፉን ቆይታ ያራዘመችው ያቀረበው ምክንያት አሳማኝ ሆኖ ስላገኘችው ነው ተብሏል፡፡
Fantahun Seifu and Mahder Assefa
እንደሚታወቀው ሰይፉ ከሸገር የሚለቀው የራሱን የሬዲዮ ጣቢያ ስለሚጀምር ነው፡፡ ‹‹ዋን ላቭ›› የተሰኘውና በመስከረም ስርጭት እንደሚጀምር የተነገረለት ይህ ጣቢያ በሰይፉ፤ በሰራዊት ፍቅሬና በአርቲስት ማህደር አሰፋ(በወንድሟ በኩል) የተቋቋመ ሲሆን የገንዘቡ ምንጭ ደግሞ ሼህ መሐመድ አልአሙዲ ናቸው፡፡

አልአሙዲ ይህ የሬዲዮ ጣቢያ እንዲቋቋም የሚያስፈልገውን የ8 ሚሊዮን ብር ካፒታል በእነሰይፉ ስም አስገብተው የንግድ ፈቃዱ ከተሰጣቸው በኋላ ብሩን መልሰው ወስደውታል፡፡ ይሁንና ማንኛውንም ለጣቢያውና ለስቱዲዮ ማቋቋሚያ የሚያስፈልገውን ወጪ እንደሚሸፍኑ ቃል ገብተውላቸው ነበር፡፡ የገቡትን ቃል እስካሁን ለማሳካት እንዳልቻሉ ምንጮቻችን ገልፀውልናል፡፡ ለሬዲዮ ጣቢያው እስካሁን ቢሮ ለመከራየት እንኳ እንዳልቻሉ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡ ለስቱዲዮ የሚሆኑ እቃዎችን ለመግዛት ከአንድ ድርጅት ጋር ተዋውለው ድርጅቱ እቃዎቹን ቢያስመጣም ከፍለው ለመውሰድ አልቻሉም፡፡ አልአሙዲ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከማህደር ጋር እየተደባበሩ መምጣታቸው ቃል የገቡትን የሬዲዮ ጉዳይ ላለማሟላት ወደኋላ እንዲሉ እድርጓቸዋል የሚሉ አሉ፡፡

ይህን ምስጢር የተረዳችው አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ የሰይፉን ቆይታ እስከመስከረም አራዝማዋለች ብለዋል ምንጮቻችን፡፡
(በዋን ላቭ ሬዲዮ የአርቲስት ማህደር ወንድም ከ60 ፐርሰንት በላይ ድርሻ አለው)

ሃብታሙ አያሌው ህመም ባሻገር ሰሞኑን በአማራ ክልል አይቼው የመጣሁት በህዝብ ላይ የሚፈጸም ግፍ

$
0
0

 

ከኢትዮጵያ ሌላ መኩሪያና መመኪያ የሌላቸው ሀገር ውስጥ የሚገኙና በዓለም ዙሪያ የተበተኑ ኢትዮጵያውያን በአሁኑ ወቅት በወያኔ የግፍ ስቃይ ደርሶበት ጣር ላይ ለሚገኘው ለአንድ ቆራጥ ኢትዮጵያዊ – ለሀብታሙ አያሌው – እያዘኑ ይገኛሉ፤ በርግጥም ይህ ብዙ ሩጫ የሚቀረው ወጣት አንዳች የማይቀለበስ ዘላቂ ጉዳት የሚደርስበት ከሆነ የሁላችንም ፀፀትና ሀዘን ነው፡፡

(ፎቶ ከፋይል)

(ፎቶ ከፋይል)

ዜጎችን ከእስር ቤት በአእምሮ፣ በኅሊናና በአካል ገድሎ በማውጣት ተወዳዳሪ የማይገኝለት የወሮበላው የትግሬው ገዢ መደብ ሕወሓት ደግሞ በዚህ የአንድ ሰው የሚመስል ግን ሀገራዊ ይዘት ባለው የጋራችን ጉዳይ ትርፍ እንደሚዝቅበት የታወቀ ነው፡፡ ሰው በአንድ ሀብታሙ ሲንጫጫ ወያኔዎች የተወሰነ እፎይታ ያገኛሉ፡፡ ወያኔ ጭርታን እንደማይወድ ግልጽ ነው፤ በምንም ይሁን በምን ሕዝብና ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ተብዬው ስለወያኔና በወያኔ ሰበብ ሲንጫጩ ደስ ይለዋል – ዕብዶቹ ወያኔዎች የሆነ ሥነ ልቦናዊ እርካታ የሚያገኙበት ይመስለኛል – “አለን፣ ገና አልሞትንም” የሚል መልእክት ለአባሎቻቸውና ለወዳጆቻቸው ለማስተላለፍ ሲሉ መሆን አለበት፡፡ ሰሞኑን እንኳን ቤት በማፍረስ ተግባር ተሠማርተው ይሄውና በክረምት – በማይሆን ወቅት – እባብና ዐይጥ እንኳን ተስማምተው በሚኖሩበት የዝናብ ወራት – ሕዝብን በገዛ ቀየው በጥይት እየቆሉ ናቸው፡፡ ይህ ዓይነቱ ሁከትና ግርግር ትልቅ መዝናኛቸው ነው፡፡ ከሀዘን አምላኪዎች (ከሳዲስቶች) ከዚህ ሌላ አይጠበቅም፡፡

ሀብታሙ አያሌው አንዱ አቤል ነው – በወንድሙ ቃየል የተገደለ፡፡ ለሀገሩ መስዋዕት የሆነ ንጹሕ በግ፡፡ ከዳነልን እሰዬው እልል በቅምጤ ነው፡፡ ካልሆነልንም በፊትም ሲናገረው የነበረው ትንቢቱ ደርሷልና ይብላኝ አሣራቸውን እያበዙ ለሚገኙት ወያኔዎች እንጂ እርሱ አንዱን መንገድ መያዙ ቢያስቀና እንጂ ሊያስቆጭ አይገባም፤ እንኳንስ የርሱን የመሰለ የክብር ሞት ቀርቶ ሰው በትንታና በእንቅፋትም ይሞታል፡፡ የሚታዘንልን እንግዲያውስ ጉድ እያየን እዚሁ ወያኔ አፍንጫ ሥር ለተጎለትነው ለእኛ ነው፡፡ መስዋዕትነት በሀብታሙ አልተጀመረም፤ በርሱም አያልቅም፡፡

ፕሮፌሰር አሥራትን የቀረጠፈ የቀን ጅብ፣ መምህር አሰፋ ማሩን የቆረጠመ ጭራቅ፣ ተማሪ ፋንታሁን ወርቁን የጎረደመ የአጋንንት ሠራዊት፣ በአሥርና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሓን ዜጎችን ከርቸሌ አውርዶ እያማቀቀ የሚገኝ የሣጥናኤል ፈረስ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወገኖቻችንን ደም ያፈሰሰና በደም ባሕር እየዋኘ ያለ የትግሬ ወያኔ ጭፍራ ይህን ወጣት ሰላማዊ ታጋይ ለህክምና ወደ ውጭ ይፈቅድለታል ብሎ ማሰብና በማንኛውም መንገድ ፈቃድ መጠየቅ ግን የወያኔን ባሕርይ ካለመረዳት የሚመነጭ የዋህነት ወይም “የበኩሌን አድርጌያለሁ” ከሚል መጠነኛ የሥነ ልቦና እርካታ የማያልፍ ከንቱ ሙከራ ነው፡፡ ጦርነት የገጠምከውን ባላጋራ “ጥይት አልቆብኛልና ካርታውን እስክሞላ ድረስ እባክህን ሳትተኩስ ጠብቀኝ” ብሎ ጠላትን እንደመለመን ነው – ይህ ደግሞ በትንሹ ሞኝነት ይመስለኛል – የበሬ እንትን ይወድቅልኛል ብላ ስትከተል የዋለችውን ቀበሮ ዓይነት ሞኝነት፡፡ ቀድሞ ነገር ከእስር ቤት አኮለሻሽተው የሚያወጧቸው ለምን ሆነና ነው? ስንትና ስንት ነገር እያወቅን እንዴት ነው ወያኔዎችን ማሰብ እንደሚችሉ ሰዎች ቆጥረን ለትዝብት የሚዳርግ ነገር የምናደርገው? ሰይጣን ምን ምሕረት ያውቅና ነው በስለት የማያገኘውን ድንቅ ነገር ለማደናቀፍ ሀብታሙን ለህክምና ወደ ውጪ የሚፈቅድለት? ሬሣውንም አይፈቅድም፤ በፈቀዱና እኔ በቀለልኩ፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሔር ተዓምር ዕፁብ ድንቅ ነውና ባለበት ምሕረቱን እንዲልክለት ወደርሱ እንጸልይ፡፡ ወያኔን ማባበሉም ሆነ ለጌቶቹ አቤት ማለቱ ጉንጭን ማልፋት ነው፡፡ አማራንና በእግረ መንገድም  የኢትዮጵያዊነትን ኩራትና ብሔራዊ ስሜት ድምጥማጡን ለማጥፋት ቆርጠው የተነሱ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ወያኔን እደግ ተመንደግ ከማለት ውጪ አንድ ሀብታሙን ይቅርና ከሚሊዮን የሚበልጥ ዜጋ በጠራራ ፀሐይ በየቀኑ ቢጨፈጨፍ ደንታ የላቸውም፡፡ እነዚህ የብዔል ዘቡል አሽከሮች ከአፍሪካውያን ተላላኪዎቻቸው ጋር እየተመሣጠሩ የዓለምን ሕዝብ ቁጥር ከዕርቦ እጅግ ባነሰ ሁኔታ አውርደው የራሳቸውን አዲስ ሥርዓት ለማቋቋም ወደ ፍጻሜ ትንቢቱ እየተንደረደሩ ስለሆነ የኛን ጩኸት ቀርቶ የገዛ ሕዝቦቻቸውን ስቃይና ዋይታ እንኳ የሚሰማ ጆሮ የላቸውም – እናም ወደላይ እንጩኽ ግዴላችሁም፡፡ በቀል የእግዚአብሔር ናትና፡፡ የሀገራችን ችግር ደግሞ ውስብስብ በመሆኑ አንድዬ ካልተጨመረበት ትርፉ ውኃ መውቀጥ ነው፡፡ ሰው እንዲልክልን ፈጣሪን ከልብ እንለምን፡፡

ይልቁንስ ጉድ ልንገርህ ወገኔ፡፡ ወያኔ ዐማራው ላይ እየፈጸመ ያለው ግፍና በደል ወደር የለውም፡፡ ሰሞኑን ወደ ገጠር ወጣ ብዬ የታዘብኩት ነገር ቅዠት እየሆነ አላስተኛ ብሎኛል፡፡ ለዚህ ነው የሞተ ተገላገለ የምለው፡፡ በዚህን ወቅት እንደኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያ ውስጥ ከመኖር ይልቅ አንድ ሞት በፀጋ ተቀብሎ መገላገል ትልቅ ዕረፍት ነው፡፡ ግን የሚፈልጉት ነገር በቀላሉ አይገኝም፡፡ ወያኔን ማየትና ስለወያኔ መስማት ኅሊናችንን እየሰቀጠጠው አካላዊው ሳይሆን መንፈሳዊውና ኅሊናዊው ኑሮ የከበደን ሞልተናል፡፡ ሀገራዊ ጣራችን ካላሳጠረልን ብዙዎቻችን ክፉኛ እየተጎዳን ነን፡፡

ለወትሮው ጄኖሣይድ የሚባለው በተቀራራቢ ፍቺ በሆነ ምክንያት አንድን የሰው ዘር መፍጀት ማለት ነበር፡፡ ይህ ሰውን በጅምላ የማጥፋት ሂደት መንስኤው በኛይቷ ሀገር እንደምናየውና በሩዋንዳ እንደተፈጸመው ዘረኝነት ሊሆን ይችላል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ አማራው አካባቢ በወያኔ እየተፈጸመ ያለው ጄኖሣይድ ግን የተለዬ ነው፤ ምናልባትም በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተከሰተ ነው ብንል ከፈጠጠው እውነታ አኳያ ትክክል ነን፡፡ በነገራችን ላይ ጄኖሣይድና  ኢትኒክ ክሊንሲንግ (genocide and ethnic cleansing) የሚባሉ አንድም ሁለትም የሚሆኑ ጽንሰ ሃሳቦች አሉ፡፡ በመናኛ ንባባዊ ግንዛቤየ ባጭሩ ብገልጥላችሁ የመጀመሪያው ይበልጡን በጭፍጨፋና ግድያ ላይ የሚያተኩር ሲሆን ሁለተኛው ግን ግድያንም ጨምሮ አንድን ጎሣ ወይም የሕዝብ አካል በማስፈራራትና በማሰቃየት፣ ማንነቱን በግድ እንዲለውጥና ራሱን እንዲጠየፍ በማድረግ፣ የሚኖርበትን አካባቢ በኃይል በመቀማት፣ ዘሩን በአስገድዶ መድፈር በግድ በመበረዝና በመከለስ የሚከናወን ሲሆን ዋና ዓላማውም መኖሪያ ሥፍራውንና መሬቱን ለወራሪው ጎሣና ባህል በማስለቀቅ ነባሩን ማውደም ነው – የሚታሰበው ለንዋይና ለመሬት እንጂ ሰው እንደአማራ ማለትም እንደዝምብ ነው የሚቆጠር፡፡ እነዚህ ሁለቱም በሀገራችን ምድር በወያኔ አማካይነት እየተፈጸሙ ያሉ ዘመን አመጣሽ ወረርሽኞች ናቸው፡፡ የኛን መጠፋፋትና ውስጣዊ ቅኝ ግዛት ከሌሎች ትንሽ ለየት የሚያደርገውና ነገሩ እስካሁንም ድረስ አልገባን ብሎ ዕንቆቅልሽ ያደረገብን የአሳዳጆችና የተሳዳጆች ማኅበረሰብኣዊ ሥነ ልቦና፣ ባህል፣ አመጋገብ፣ ሃይማኖት፣የዘር ግንድ፣ የቋንቋ መሠረት፣ አስተሳሰብ፣ ትውፊት ወዘተ. ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ መሆኑ ነው፡፡ የሌሎችን ስናይ እንደኛ ያለ ተመሳስሎ አይታይባቸውም፡፡ ለምሣሌ የሩዋንዳውያኑ ሁቱዎችና ቱትሲዎች በመልክም በቁመትም እንደሚለያዩ ይታወቃል – ቀጠን፣ ረዘም፣ አፍንጫው እንደፖል ካጋሜ ሰልከክ ብሎ ካየኸው ቱትሲ ለመሆኑ ተጨማሪ ማረጋገጫ ላያስፈልግህ ይችላል፡፡ አጠር፣ ወፈር፣ ደልደል፣ ጠንከር፣ የበላውን ቁርስ ደፍጠጥ ባለው የአፍንጫው ቀዳዳ የምታይ ከሆነ ደግሞ ሁቱ መሆኑን ትገምታለህ፡፡ በቋንቋና ሃይማኖት እስከዚህም እንደማይለያዩ ይነገርላቸዋል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ስትመጣ ግን የዐድዋውን ሐጎስ ከመራቤቴው ድፋባቸው ለመለየት ነጭና ጥቁር ክር ግምባራቸው ላይ ካልታሰረላቸው በስተቀር አትችልም – (በሶማሌ የጦፈ የጎሣ ግጭት ወቅት አንዱን ከአንዱ ለመለየት ተቸገሩና አንድኛው ጎሣ የሆነ የቀለም ኮድ መርጦ በጨርቅ ምልክት መግባባት ጀመረ አሉ፡፡ ያቺ ምሥጢር ትሾልክና ጠላት እጅ ትገባለች አሉ፡፡ እነዚያ ጎሣዎች ያን ጨርቅ ልክ እንደነሱው ያስሩና በዚያ መንደር ገብተው ተቀናቃኛቸውን ጎሣ ረፈረፉት አሉ፡፡ ደግ ለ“አሉ”፡፡ እጅግም መመሳሰል መጥፎ ነው፤ ያስጠቃል፡፡ የኛ ዋና ችግር እኮ ይሄው ነው!)

ከፍ ሲል የተገለጹትና በተለያዩ ጎሣዎች መካከል የሚፈጸሙ የጥፋት መንገዶች ዓለም የሚያውቃቸውና ሰለባዎቹም ባዘኔታ ከንፈር የሚመጠጥላቸው ናቸው፡፡ አሁን እያየነው ያለነው ወያኔ በአማራ ሕዝብ ላይ እያደረሰው የሚገኘው ውድመት ግን በየትኛውም የዓለም ታሪክ ያልተመዘገበ ስም እንኳን የማይገኝለት ነው፡፡

በገጠር አካባቢ አማራው ላይ የወደቀው ማይምነትና ድንቁርና የተለዬ ነው፡፡ ሕዝቡ ላይ የተጣለበት ድህነት ወደር አይገኝለትም፡፡ እነዲኬቲና ሜሪስቶፕስ የተሰኙ ሥነ ተዋልዶ ላይ የሚሠሩ መያዶች እንኳን በምዕራባውያን ጌቶቻቸው ይሁንታና በወያኔ ግፊት መሠረት እንደልባቸው የሚፈነጩትና ዜጎች ዘራቸውን እንዳይተኩ በአነራዊ መርፌ የሚያመክኑት በአማራው አካባቢ ነው – ለደደብነቴ ይቅርታ ይደረግልኝና ትግሬ ሴቶች ሲወልዱ የሚሸለሙ ይመስለኛል፡፡ የአማራው ከተሞች ከልማትና ከዘመናዊ የአስፋልት መንገድ የፀዱ ናቸው፡፡ ቤቶቹ ፈራርሰው እንዳይወድቁ በአጠናና በሐረግ ተይዘዋል፤ ቆርቆሮው ወንፊት ሆኖና በእርጅና ምክንያት በስብሶ በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሣር ቤት የሚሩ ከተመኞች የሚታዩት በአማራው አካባቢ ብቻ ነው፡፡ የትግራይዋ ኩንስንስ ዋጃ ከተማ ከአማራው ቀብራራ ደብረ ማርቆስ ትበልጣለች – ምክንያቱም ከየቦታው እየዘረፈ እሷን የሚያከብር ሕወሓት የሚባል ወምበዴ ድርጅት አላት፡፡ እነደብረ ማርቆስና እነ ደብረ ታቦር ግን የእንጀራ ከተሞች ናቸው – ጥፋት የተደገሰላቸው፡፡ አንድን የሚጠሉትን ሕዝብ ሲቻል በጥይትና በበሽታ፣ ያ ባይቻል በተዘዋዋሪ በርሀብና በችጋር በመጥበስና በማይምነት በማደንቆር ቀጥቅጦ መግዛት የልብን እንደሚሞላ ወያኔዎች በተግባር እያሳዩ ናቸው፡፡ አለሁህ ባይ የሌለው ባይተዋሩ የአማራ ሕዝብ በየገጠሩ እየገፋው የሚገኘው መራር ሕይወት ይህን ይመስላል – በወፍ በረር ቅኝት፡፡

የአማራ ልሂቃን ተብዬዎችን ከሥር መሠረቱ ለማጥፋት የሚፈልቁበትን ሕዝብ በሥልት ማጥፋቱን ወያኔው ተያይዞታል – ባሕሩን እስከወዲያኛው በማድረቅ አንድም የአገዛዝ ተቀናቃኝ እንዳይፈጠር ለማድረግ በታለመ የጅሎች ፈሊጥ፡፡ የማን ምክር መሆኑ ደግሞ ግልጽ ነው፡፡

ስለዚህም በአማራው አካባቢ እኔ ነኝ ያለ ዲግሪ ጭኖ ስሙን አስተካክሎ የማይጽፍ “ምሁር” ብታገኙ እንዳትደነቁ፡፡ በአማራው አካባቢ አስተሳሰቡ ከአፍ እስካፍንጫው የማይደርስ ምሁር በዲግሪና ዲፕሎማ ተምበሽብሾ ታገኛላችሁ፡፡ እንግሊዝኛን ቀርቶ አማርኛን በቅጡ መናገር የማይችል አማራን ማየት ዛሬ ዛሬ ያልተለመደ አይደለም፡፡ የወያኔ ሤራ ግቡን እየመታ ለመሆኑ የአማራን አካባቢ በመጎብኘት ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ አገር ምድሩን በነፈዝ ዜጋ እየሞሉት ነው፡፡ ራሳቸው ኤቢሲዲን ሳይለዩ በሁለተኛ ደረጃ እንዲያስተምሩ የተመደቡ “መምህራን”ን አይቻለሁ፡፡ ተማሪው ፉዞ፣ መምህሩም ፉዞ፣ ርዕሰ መምህሩም ፉዞ፣ ሁሉም ዜሮና የፉዞ ፉዞ፡፡ ተዋርደናል ጎበዝ! …

የአማራን አካባቢዎች በግልጽና በሥውር እያስተዳደሩ የሚገኙት ትግሬዎች መሆናቸውን ደግሞ መርሳት የለባችሁም፡፡ ትግራይ ውስጥ በአንድም የመንግሥት መሥሪያ ቤት አማራ በኃላፊነት ቀርቶ – ይበልጡን ከቴክኒክ ሥራዎች ውጪ ማለት ነው –  በተራ የቢሮ ሠራተኝነት እንደማይገኝ ሳንነጋገር የምንግባባ ይመስለኛል፡፡ በአማራው ክልል ግን ፈላጭ ቆራጩ ትግሬ ነው፤ ብአዴን ተብዬው ከኮንዶምነት አያልፍም – እንደኮንዶም የሚለጠጥ ሆዳም የላስቲክ ጓንት፡፡ በብዙ የአማራ አካባቢዎች ምርጥ ምርጡ የከተማና የእርሻ ቦታዎች ለትግሬዎች የሚሰጡ የቅኝ ገዢዎች አንጡራ ሀብት ናቸው፡፡ አማራው ሕዝብ የተረፈው በየከተሞቹ የሚደመጡ የትግርኛ ዘፈኖች ብቻ ናቸው – የከበሮ ድለቃ፤ እልፍ ሲልም ጥቂት የኮብልስቶን መንገዶች፡፡ በኖኅ የውኃ ጥፋት ዘመን ወያኔን መሰል የኃጢኣት ማኅደሮች የተራራና የትላልቅ ዛፍ ጫፎች ላይ ከነከበሯቸውና እምቢልታቸው በመውጣት በውኃው እስኪሰምጡ ድረስ እንደትግሬዎቹ ይደልቁ ነበር ይባላል – ታሪክ ራሱን ደግሞ አሁን ወያኔዎች በመላዋ ኢትዮጵያ መሬት ጠባቸው እየደለቁ ናቸው – መልካም ድለቃ፡፡ ልክ እንደ አዲስ አበባው ሁሉ በአማራው አካባቢም ይህንን ነው የታዘብኩት፡፡ “ከተራበ ለጠገበ አዝናለሁ” ይላል የተረት አባቱ አማራ፡፡ ለነገሩ ዱሮም በልጅነቴ “ትግሬ ጥጋብ አይችልም” ሲባል እሰማ ነበር – አሁንም እምብዝም ላልተለመደ ግልጽነቴ ይቅርታ፡፡ አሁን እኔም እንዳቅሚቲ “ጥጋቡን የሚቆጣጠር ብፁዕ ነው” ብዬ ብተርትስ? አዎ፣ ጥጋብን በልክ ማድረግ የፈጣሪን መንገድ እንድንከተል ከማስቻሉም በላይ ሰው መሆን ምን ማለት እንደሆነ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡ የተራበ መጥገቡ፣ የጠገብም መራቡ ያለና የነበረ ነው፡፡ ትናንትን ማየት የማይችል ስለነገም ዕውር ነው – ዛሬ የያዝነው የሚመስለን ነገር ነገ ይንሸራተትና ወደ ጎረቤታችን ሊሄድ ይችላል፡፡ ማንኛውም ዓይነት ዕውርነት ደግሞ ላልታሰበ አደጋ ይዳርጋልና የውስጥ ዐይናችንን ገልጠን ዙሪያ ገባችንን እንመልከት፤ ከወደቁ በኋላ ወዬው ከማለት ሳይወድቁ በፊት መጠንቀቅ ይቻላል፤ ይህ ደግሞ ተገቢና አስተዋይነትም ነው፡፡ አንጎልን ካደራበት የጥጋብና የዕብሪት ሞራ ነጻ ማውጣት በቅድሚያ የሚጠቅመው ራስን ነው፡፡

ከፍ ሲል ለመግለጽ እንደሞከርኩት በዚህች መጣጥፍ መልእክቴ ባጭሩ አማራው በቁሙ ሞቷል እያልኩ ነው፡፡ የተማረ ዜጋ እንዳይኖረው፣ ተቆርቋሪ ዘጋ እንዳያፈራ፣ ተረካቢ ዜጋ እንዳይኖረው፣… ሆን ተብሎ በተጣለ የማይምነት ደዌ እየተለከፈ ያልተማረው ቀርቶ ተማረ የተባለው ሳይቀር ጠብደል ማይም እየሆነ ነው፡፡ መምህራንን አየሁ፤ ተማሪዎችን አየሁ – ሁሉም በሚያሳዝን ደረጃ በማይምነት ልምሻ ተመትተዋል፤ ትምህርት ቤቶች የፈራረሱና አንድም ግብኣት የሌላቸው ናቸው፤ የተተው ምድረ በዳዎች ሆነዋል፡፡ አንድን ሕዝብ ከዚህ በላይ መግደል አይቻልም፡፡ አማራው ክልል ውስጥ ተቀምጠህ ትግራይ ውስጥ ያለህ ያህል ይሰማሃል፤ ፍርሀትን አንግሠው፣ ጆሮ ጠቢን በሰው ልክ አሰማርተው፣ … አማራው ተጨብጦና ተኮራምቶ በርሀብና በርዛት እንዲያልቅ እያደረጉት ነው – ለወትሮው አማራው የሚፈናቀለው ከሌሎች የኢትዮጵያ ግዛቶች ነበር፤ አሁን ግን ከራሱ ቄ በትግሬዎች እየተፈናቀለ ነው – ለእነእንትና ቢመር ቢጎመዝዝም እውነትን አንሸፋፍን፡፡ የመጣ ይምጣ እንጂ እነእንትናን ለማስደሰት ብዬም እውነትን ከመግለጥ አላፈገፍግም፡፡

ይህ እንግዲህ ሰው የሚያውቅላቸውንና የማያውቅላቸውን በአማራው ላይ የሚፈጽሙትን ዘርን በመርፌ እስከማምከን የሚደርሰውን ወንላጀቸውን ሳይጨምር ነው፡፡ ሌላ ሌላውን ታሪክ፣ ታሪክ ራሱ ወደፊት ያወጣዋል፡፡ ትግራይ ከፍላ የማትጨርሰው ዕዳ ውስጥ እየተዘፈቀች እንዳለች በበኩሌ ይሰማኛል፤ አማሮችስ ተገላገሉ፡፡ አረረም መረረም ማመራቸውን ተወጡ፡፡ የማን ዕዳ መሆኑ ወደፊት የሚታይ(የሚጣራ) ሆኖ እነሱ ግን በምድርም በሰማይም ያልተፈጸመ ግፍና በደል በትግሬ ወያኔዎች እንደዶፍ ወረደባቸው፡፡ በስማም እንደተባለበት ሰይጣን ፈዘውና ደንግዛው ዝም ብለው ዋጧት፡፡ እናም ከአሁን በኋላ ጨለማውና ጭጋጉ እየገፈፈ እንደሚመጣላቸው መተንበይ እችላለሁ፡፡ ግን እነሱም ይወቁበት፡፡ እንደትግሬዎቹ በበቀልና በጥላቻ ተሞልተውና በዱባ ጥጋብ ታውረው በተመሳሳይ መንገድ የሚነጉዱ ከሆነ የነጻነታቸው ቀን ይርቃል – ከናካቴውም የነፃነት ቀን የሚባል ነገር ላይመጣ ይችላል፤ ወደፈጣሪ ተመልሰው የውስጣቸውንም የምቀኝትና የተንኮለኝነት ክርፋት በቅንነትና በደግነት ጠበል አጥበው ወደ እግዚአብሔር ከተማጠኑ ነፃነታቸው በደጅ ቆማለች – ወንድም በወንድሙ ላይ ማስተብተቡንና በደንቃራና በመተት አውጀምጅም መጠላለፉን፣ ጧት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ደጅ መጥናቱን፣ ከሰዓት በለጥሻቸው አድባር መፈናደሱን ትተን በትክክል ወደ አምላክ ከተመለስን አንድዬ ቅርብ ነው፡፡ አንዳንድ አክራሪዎች እንደሚሰብኩት አማሮች አማራነታቸውን የማወቅ ግዴታ የለባቸውም፡፡ በኢትዮጵያዊነታቸው ግን አንድ ሆነው እርስ በርስ ሳይናናቁና “አንተ ሸዌ፣ አንተ ጎንደሬ፤ አንተኛህ ጎጃም አንተኛህ ወሎ” ሳይባባሉ ባንድነት መታገል አለባቸው፤ የዓለም አቀፉ የጥቃት ጦር ዋና ዒላማ እነሱ ስለሆኑ ሌሎች ወንድምና እህቶቻቸውን አስተባብረው ከዚህ አገርን በቁም ከሚሸጥ የወያኔ ግሪሣ ራሳቸውንም ሀገራቸውንም ነፃ ለማውጣት መታገል ይገባቸዋል፡፡ ሀገረ ማርያምንም ወደ ቦታዋ መመለስ ይኖርባቸዋል፡፡ ኢአማኒ ጉድሽ! እንዲህ በል አለኝ፡፡ አልኩ፡፡

ስለዚህ አንድ ሀብታሙ ታመመ፣ ሞተ … የሚለው ነገር ከዚህ ታዝቤው ከመጣሁት ዘግናኝ እውነት አንጻር ሲታይ በርግጥም የምንገኝበት የታሪክ አንጓ እጅግ አሳሳቢ እንደሆነ እንረዳለን፡፡ ጊዜ የለንም፡፡ ይህን ሕዝብ ለማዳን ዕድሉና አጋጣሚው ያላችሁ ሁሉ የምትችሉትን ሁሉ አድርጉ፡፡ ከሰው የሚቻለውን አድርጉ እንጂ ቀሪውን የኢትዮጵያ አምላክ ይጨርሰዋል፡፡ አምላክ ኢትዮጵያን እስከወዲያኛው ትቷት አያውቅም፡፡ የአሁኑ ለየት አለ እንጂ ዱሮም ወደዚህ የሚጠጋ ችግርና የመከራ ወቅት ይከሰት ነበር፡፡ ስለሆነም እኛ ወደርሱ ስንመለስ እርሱም ወደኛ ይመለሳልና ከኛም እንዳይቀር የምንችለውን ሁሉ ከልብ እናድርግ፡፡ ሁሉን ለርሱ መጣል የማይቻል መሆኑን ለማጠየቅ ለአዳምና ለሔዋን የነገራቸው “ አዳም ሆይ፣ በላብህና በወዝህ ለፍተህ ደክመህ ብላ” የሚለው ቃል ኅያው ምሥክር ነው፡፡ ተዓምርን ብቻ አንጋጦ የሚጠብቅ ሕዝብ ደግሞ “ሰነፍና ሣይዋጋም የተሸነፈ ነው” እንደሚባል እንወቅ፡፡ በቃ፡፡

ጵጵስናና ፈተናው –ክፍል ሁለት

$
0
0

Holy sinod addis ababa

በአለፈው ጽሁፋችን የቤተክርስቲያንን መከፋፈልን እንደመልካም አጋጣሚ ቆጥረው ክፍፍሉን የሚያጠናክሩ ሰዎችና፤ የጵጵስና ተግዳሮቶችን / ፈተናዎችን/ ለመዳሰስ ነጥቦችን በይደር ማስቀመጣችን ይታዎሳል ። ችግሮቹንና ከችግሮቹው ጀርባ ያለው በጎ ገጽታ በሁለት ምድብ ከፍለን እንቃኛለን። ለዛሬው ከችግሮቻቸው እንጀምር።
ችግሮቹና የችግሩ ባለቤቶች
የመጀመሪያዎቹ የአቢያተክርስቲያናት መከፋፈል የሚያመጣውን ጉዳት የማያውቁ ፤ ከክፍፍሉ በኃላ የተፈጠሩ ወይም የተገኙ በአንድም በሌላ ምክንያት ወደአካባቢው የፈለሱ ናቸው። እነዚህ በአሉበት አካባቢ ቤተክርስቲያን የሚገለገሉ ሁነው ያሉበት ቤተክርስቲያን በምንምክያት እንደመሰረተ የማያውቁ ናቸው። እነዚህ በተለምዶ ገለልተኛ የሚባሉት ናቸው ስለገለልተኛ ጥሩነት የተሰበኩ ሲሆኑ ካህኑን በገዘብ እየገዙ ማን ይሹመው፣ ከየት ይምጣ ፣ ሳያጣሩ የጳጳስ ስም መጥራት የሌለበት መሆኑን ነግረው የቀጠሩበት ቦታ ማለት ሲሆን ። ይህ ቦታ በባለ አባቶች ወይም የቦርድ ሜምበር የሚመራ የሚመስል ፤ አንዳዶቹ የእድሜልክ ፣አንዳዶቹ ሃላፊነትን በማሸጋሸግና ጊዜ በመቀያየር የሚያዙበትና የሚናዝዙበት ቦታ ነው። አገልጋዮችንም እንደ ቤተክርስቲያን ህግ ሳይሆን የሚመሩት መስሎ የመኖር ያዋቂ አጥፊ የሚባሉት አይነቶች ናቸው። የእነዚህ ሰዎች አባላት በቅዳሴው ላይ እግር ጥሏቸው: እነሱን ወደ ማይመስል በስደት ወይም በሀገር ቤት በአለው ሲኖዶስ በሚመሩት ቤተክርስቲያን ሲሄዱ መጠነኛ ለውጥ መኖሩን የሚሰሙና ያሉበት የተሻለ እንደሆነ አምነው የሚኖሩ ናቸው። ከእነሱ ውጭ በአሉት አቢያተክርስቲያናት የሚገለገል ሃጢያተኛ የሚመስላቸውም አይታጡም ። የሚበዙት የመሃል አገር የሚባሉት ሰዎቸ ቤተሰቦች ናቸው። እነዚህ በሃገር ቤትም ሆነ በውጭ ያለውን ሲኖዶስ በመንቀፍ የሚቀድማቸው የለም። አንድ ጳጳስ ተሳሳተ ተብሎ ሲነገር እነሱ ያለ ጳጳስ መኖራቸው እንደጄብድ የሚቆጥሩ ሁነዋል ። እነዚህ የችግሩ አካል የፈጠረውን ክፍተት የሚያሰፉ በእውቀትም ያለእውቀትም የቤተክርስቲያን አንድነትና ጽናትን የሚፈታተኑ ሁነዋል፡፡ ለነገው ትውልድ አንድነት ፈተና እንዲሆን ታስቦ በተከፈተው ጎዳና የሚጓዙ ናቸው።
ሁለተኛዎቹ በማህበራዊ ኑሮ አብረው የሚኖሩ ግን እኔበልጥ እኔበልጥ፤ እኔን ስሙኝ እኔ ስሙኝ የሚሉ ሰዎቸ ይበዙበታል:: ይህ ቡድን ቤተክርስቲያንን እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ ፖለቲካውንም፣ በማሃበራዊ ኑሮውንም፣ በጋራ አጣምረው መምራት የሚፈልጉ የሚበዙበት ነው። ሃይማኖታቸውን ብቻ ማራመድ የሚፈልጉሰዎች በቁጥር አንሰው ግብግብ የሚፈጠርበት ቦታ ነው ማለት ይቀላል ። በዚህ ቦታ የሚነሳው ነገር በቀላሉ የማይበርድ ይሆናል ። የፓርቲውም የመንደሩም ጉዳይ ተጨማምሮ አብረው የኖሩት ለመቃብር እንኳን የማይቆሙበት ደረጃ ይደርሳሉ። ይህ ጉዳይ አሁን አሁን ነገር አዋቂዎች የሚያቀጣጥሉት እሳት እየሆነ ነው። በጥብቅናና በአስተርጓሚነት፣ በነገር አዋቂነት ስም ጠቀም ያለ ገንዘብ ማግኛና የጊዜ ማሳለፊያም ወደመሆንም እየተሸጋገረ ሂዷል ። እነዚህ ሰዎች ጳጳሳትን የሚፈልጉት ለቡራኬ ብቻ ነው። አስተዳደራቸውም መንፈሳዊም አለማዊም አይደለም ።
ሦስተኛው እጄ ረጅሙ እግረ አጨሩ መንግሥታችን የሚጫወተው ጌም ነው።
በስደት ያለው ህዝብ በሚሰማውም ይሁን በየጊዜው እያደገ በሄደው የዘር ክፍፍል መንግሥትን አጥብቆ እየጠላ ነው በመሆኑም ይህን ጥላቻ ለመቀነስ ብዙ አባላትን በውጭ ሀገር ማፍራት እንደ ትልቅ ግብ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ነው። አባላቱን የሚመለምልበት ስልት ደግሞ እየረቀቀ ሂዷል። አሁን ጠንካራ ሰዎችን ለመልመል በቀላሉ አልተቻለም በመሆኑም በዋናነት በህዝቡ ውስጥ አለመተማመን እንዲኖር አሉቧልታ የሚያወሩ ሰዎችን በቀጥታም በተዘዋዋሪም ማብዛት ነው።ይህ በተሳካ ሁኔታ የሄደ ይመስላል ለመንግሥት የሚቃዎሙ የሚመስሉ አውቀውም ሳያውቁም ለመንግሥት የሚሰሩ በርካታ ናቸው። መጀመሪያ ሀገርቤት የሚመጣው በሙሉ የወያኔ ቅጥረኛ እንደሆነ አድርጎ ማስወራት ከተቃዋሚው ጎራ እንዳይቀላቀል ቢቀላቀልም እንዳያምኑት የሚያደርግ ነው። ሁለተኛው እከሌም እከሌም ወያኔ ነው ብሎ ማውራት ይህ የተወራበት ሰው እየቆየ ሲሄድ በእልህም ቢሆን በማህበረሰቡ በሚደርስበት ጫናና መገለል የወያኔ አባል እንዲሆን ማመቻቸት ነው። ይህን የሚያደርጉት ሰዎች ለረጅም ጊዜ ተቀዋሚ የሚመስሉ፤የሀገር ፍቅር አለን የሚሉ ናቸው እነዚህ ሰዎች የነሱን ሃሳብ የማይደግፈውን በሙሉ ወያኔ ነው ብለው ማውራት እንደልምድ አድርገውታል። በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሚሰሩት ለመንግሥት ነው። የሚበዙት ቤተክርስቲያን የሚሄዱት ቅዳሴ አልቆ ቡና ሊጠጣ ሲል ነው ተሎ ወደቤታቸው አይመለሱም፣ ነገር ይፈልጋሉ ጊዜ የሚያሳልፉበት። እነዚህ የቤተክርስቲያን አንድነትን ከሚፈታተኑት ዋናዎቹ ሁነዋል ። ቤተክርስቲያኒቱን የሚፈልጓት ሰዎች ለማግኘት ብቻ ነው ሰላሟና አንድነቷ ለእነሱ ፋይዳ አይሰጣቸውም። ጳጳሳቱን ለማዘዝ እንጅ ለጳጳሳቱ ለመታዘዝ አያስቡም።

አራተኛው የጳጳሳቱ አቀም ውሱንነት የሚፈጠረው ነው፡፡
ብዞቹ አባቶች ህዝቡን እንዴት እንደሚመሩት አያውቁም። የአስተዳደር ልምድ ብቻ ሳይሆን እውቀትም ያሳቸዋል ።ቸግር ሲከሰት እንዴት ማለፍ እንዳለባቸው አልተረዱም፣ ከችግሩ ጋር አብረው ይነጉዳሉ ፡፡ ፖለቲካውን አያውቁትም ለምን እነደሚፈልጋቸው እንኳን አይገነዘቡም። በመሆኑም ከፖለቲከኞች ጋር የማይመጣጠን ጋብቻ ይፈጥራሉ። ጓደኛቸውን የገፋውን ወንበር ይሻማሉ ፡፡ ለህጉ ሳይሆን ለሥልጣኑ የሚያደርጉት ግብግብ በህብረተሰቡ ዘንድ የነበራቸውን ክበር ቀንሶባቸዋል። ቃላቸውን የማይሰማና የማይታዘዝ አማኝ እንዲበዛ አስተዋጾ አድርጓል። የአስተዳደር ብቃታቸውም ዘመኑን ያማከለ አይደለም። ይህ ሃይማኖቱን ለማዳከም ለሚሰሩ ሰዎች እንደጥሩ አጋጣሚ ሁኖላቸዋል። እነዚህ አባቶች እነማናቸው? ምልክታቸው ምንድ ነው? በምን እናውቃቸዋለን? ለምትሉ እንመለስበታለን። እነዚህ ጳጳሳት ከእነሱ ተሽለው ሊሰሩ የሚችሉ ጳጳሳትን ሥራ በማደናቀፍ ይታዎቃሉ። አለመቻል ብቻ ሳይሆን ሊሰራ የሚችለውንም አያሰሩም። የሚበዙት ደካማ ቢመስሉም ጠካራና የሰራ ሰዎች ግን አሉን ይኖራሉም፡፡
አምስተኛው በውጭ ሲኖዶስና በሃገር ቤት ሲኖዶስ የሚተዳደሩ አቢያተከርስቲያናት መዘዝ።
በሀገር ቤቱ ሲኖዶስ የሚተዳደሩት የሚበዙት ትግረኛ ተናጋሪዎችና ያለውን ሥራዓተ-መንግስት የሚደግፉ ናቸው ።ትግረኛ ተናጋሪዎቹ ሥራዓተ-መንግሥቱን የሚቃዎሙ ቢሆኑም እንኳን ወደነዚህ መሄወዱን ይመርጣሉ። ጉዳይ ከፖለቲካ አልፎ ጎሳዊ የመሆን ዝንባሌን ያሳያል፡፡ ጳጳሳቱንም ከፋፍለው ነው የሚቀበሉት ፡ ሃይማኖትና ፖለቲካ መለየት ተስኗቸዋል ። ለትግረኛ ተናጋሪ ጳጳሳት የማድላት አባዜም ይዟቸዋል ። አኩስም የክርስትና ማእከልነቷንና መሪነቷን በዘመን አመጣሽ ፖለቲካ ወደመንደር ይዛው የገባች ትመስላለች ።
በውጭ ሲኖዶስ የሚተዳደሩ አቢያተክርስቲያናት አብዛኛዎቹ አማረኛ ተናጋሪዎችና ሥራዓተ-መንግሥቱን የማይደግፉ ብሉም ጎንደሪዮች ይበዙበታል አማረኛ ተናጋሪዎቹ የመንግሥት ደጋፊዎች ቢሆኑም እንኳን መሄድ የሚፈልጉት ወደእነዚህ ነው። ይህም ከላይኛው አስተሳሰብ የተለየ አይደለም። ከዚህ ላይ የሚደነቁት ኦሮሞኛ ተናጋሪዎቹ ናቸው ቁጥራቸው ያነሰ ቢመስልም ቦታ አይመርጡም ወደአቀረባቸው ቤተክርስቲያን ይሄዳሉ። ፖለቲከኞቻቸው ቤተክረስቲያን የነፍጠኞች ናት ቢሉም፤ ፕሮቲስታቶቹም ኦሮሞ የጴጤ ነው እያሉ ቢወተውቱም፤ እነሱ ግን አልሰሟቸውም እንዴውም ጥንካሪያቸው ጨምሮአል ፡፡ ከላይ የተጠቀሱት፣ በሁለት አቅጣጫ የቆሙ አቢያተክርስቲያናት፡ የሚመሩት በጳጳሳት ቢመስሉም ስደቱ የፈጠረው የፖለቲካ መተራመስና የባህል ተቃርኖ ሚዛናቸውን አዛብቶታል። ያለ ጳጳስ ከሚኖሩትና በሦስተኛ ወገን ከቆሙት ግን በእጅጉ ይሻላሉ
ስድስተኛው ማኀበረ ቅዱሳንና አንቲ ማኀበረ ቅዱሳን ብሎም ተሃድሶዎቹ እየሄዱበት ያለው መንገድ ነው
ማኀበረ ቅዱሳን የሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያለው እንቅስቃሴው የተለያየ እንድምታ አለው:: በውጭ ያለው ፖሊሲው ብዙ ተቃርኖ የበዛበትና ብስለት በሌላቸው ሰዎች የሚመራ የሚመስል ፤ ጥንካሬውም የተሻፈፈ ከነገሮች ጋር የተላተመ ነው። ማኀበሩ በተጀመረ ጥቂት ዓመታት ውስጥ የተከተላቸውና ጥቂት የማይባሉ ጣላቶችን ያፈራበትን ዓመታት ዋጋ ያስከፈሉት ይመስላል። የማኀበሩ የውጭ አመራር በአርቆ አሳቢነት ቢሄድ ኑሮ በውጭ ያለችውን ቤተክርስቲያን ይበልጥ ይረዳ ነበር። ነግር ግን በጉንጭ አልፋ ክርክር ጊዜ አባክኗል። ብዙ ለቤተክርስቲያን አንድነት የሚጠቅሙ ሃሳቦችን በወጣቱ በኩል ማስረጽ ሲችል ቤተክርስቲያን በግል ወደመክፈትና ልዩነት ወደማጠናከር አጋድሏል። አላስፈላጊ ጥላቻዎችንም አትርፏል። በጅምላ ሰዎችን መክሰሱና ራሱን ብቸኛ የሃይማኖቱ ተቆርቋሪ አድርጎ ማሳየቱም አልተወደደለትም፡፡
ይልቁንም ተሰሚነት ያላቸው አባቶች ይዞ ከመስራት ይልቅ እራሱን ለማስቀደም የሄደበት መንግድ አደገኛ ሆኗል ።በሀገር ቤት ከሚሰራው አንጻር ሲገመገም የውጭው የተሳካ አይመስልም።አንቲ ማኀበረ ቅዱሳን የሚባሉት ደግሞ…
ይቀጥላል
ከሊቀ መራህያን
ማንኛውም ሰው እውነቱን ማወቅ ከፈለገ በንጹህ አይምሮ በዚህ እሜል ሊያገኘኝ ይችላል jemis1968@gmail.com


ከኢትዮጵያ ቋንቋዎች አንዱ የሆነው ኦሮምኛ ቋንቋ መጻፍ ያለበት በግእዝ ፊደል ወይስ በላቲን ፊደል? – ክፍል 2

$
0
0

MH Leulekal Akalu

6/29/2016

(ከኢትዮጵያዊ ማንነት አንጻር ለውይይት መነሻ እንዲሆን የቀረበ)

 

ይህ አጭር ጽሑፍ ቪዥን ኢትዮጵያ እና ኢሳት ባዘጋጁት መድረክ ላይ ምሁራን ከላይ በርሱ ሰለተጠቀሰው ርዕሰ ጉዳይ  ኦረምኛ በላቲን ፊድል እንዲጻፍ ያስፈለገበት ምክንያት ምን ነበር? በሚል ለቀረበው ጥያቄ ሦሰት ምሁራን በተሰጡአቸው  መልሶች ላይ  ፥ውይይትን የሚጋብዝ ፥ሐተታን [1] ያካተተ ጽሁፍ ነው። በዚህ  ጽሁፍ ለምሳሌ ያክል ኦሮምኛን እንደ ምሳሌ አነሳን እንጅ የጽሑፉ አላማ ማንኛውም የሀገራችን ቋንቋ በሀገርኛ ፊደል እንጅ በባእዳን ፈደል መጻፍ የለበትም የሚለውን በበቂ አመክንዮ[2] ላይ የመሠረተ  ሀሳብ ለማሳየት የተጻፈ ነው።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

በምስራቅ ሐረርጌ አወዳይ ከተማ የ9 ዓመት ልጅን ጨምሮ 5 ሰዎች ተገደሉ

$
0
0

aweday city2 aweday city

(ዘ-ሐበሻ) ዛሬ ጠዋት በአወዳይ ከተማ በአንድ መደብር ላይ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ የ እሳት ቃጠሎ መነሳቱን ተከትሎ የእሳት አደጋ በቶሎ ባለመጣቱ ህዝቡ ተረባርቦ እሳቱን በማጥፋት ላይ እያለ ፌደራል ፖሊስ ሕዝቡን ለመበተን ባስነሳው ጥይት ተኩስ የተነሳ በተጀመረው ብጥብጥ የ5 ሰዎች ሕይወት ማለፉን እና ከነዚህም መካከል የ9 ዓመት ህፃን ልጅ እንደምትገኝ የደረሰን መረጃ አመለከተ::

ሕዝቡ እሳት አደጋው እንደተነሳ ወደ እሳት አደጋ መከላከያ ስልክ የደወለ ቢሆንም በ እሳት አደጋው ፈንታ የመጣው ግን ፖሊስ ነበር:: እንዴት ከ እሳት አደጋው የፖሊስ ሃይል ሊመጣ ቻለ በሚል ህዝቡ ተቃውሞውን ማሰማት የጀመረ ሲሆን ፌደራል ፖሊሶችም ወደ ህዝብ መተኮስ መጀመራቸውና ከሞቱት 5 ሰዎች በላይም በርካታ ሰዎች መቁሰላቸው ተሰምቷል::

በዛሬው ዕለት በፌደራል ፖሊስ የተገደሉት 5 ሰዎች ዝርዝር
1ኛ. ፋንዲሼ ናስር
2ኛ. ፍርሞሳ አሃምዳስቅ
3ኛ. ሙና ቱርኪ
4ኛ. ኦባሳ ያሲን
5ኛ. ሰይፈዲን አብዱሳቡር ናቸው ተብሏል:: የሞቱት ወገኖችም ሃሮማያ ሆስፒታል አስከሬናቸው መላኩም ተረጋግቷል::

እነዚህ 5 ሰዎች ከተገደሉ በኋላ ተቃውሞው ወደ ሌሎች ቦታዎች መዛመታቸው የተሰማ ሲሆን በሃሮማያና በተለያዩ የምስራቅ ሃረርጌ ትናንሽ ከተሞች ሕዝቡ አደባባይ ወጥቶ ተቃውሞውን እያሰማ ነው::
ይህ

“ሰብሰብ በሉ” የኢትዮጵያውያን የባህል ስብስብ በቶሮንቶ

$
0
0

ethiopian Girlsልጆቻችን ባህላቸውን ታሪካቸውን እና ቋንቋቸውን በአጠቃላይ የመጡበትን ሲያውቁ በራሳቸው ይኮራሉ።

ለዚህም ስል ከልጆቼ ጋር ሆኘ “ሰብሰብ በሉ” የኢትዮጵያውያን የባህል ስብስብን መሰረትኩ።

እኤአ ከ2009 ዓም ጀምሮ በተቋቋመው ስብስብ አማካይነት ወጣቶች በየቦታው እየተዘዋወሩ ባህላዊ እና ታሪካዊ ትርዒቶችን እናሳያለን። ልጆቻችን በማህበረሰቡ አድናቆትን አትርፈዋል ይላሉ መስራችዋ ወይዘሮ ሶስና አሰፋ ።

በሰሞኑ የሰሜን ኣሜሪካ ኢትዮጵያውያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫልም ላይ ስብስባቸው እየተሳተፈ ነው።

ከቡድኑ መስራች ወ/ሮ ሶስና አሰፋ ጋር የተደረገ ቆይታ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

 

የ12ኛ ክፍል ሃገራቀፍ ፈተና መሰረቅ ተከትሎ በርካታ ቀውስ ፈጥሯል ኣልፈዋል ኣሁንም እየፈጠረ ነው።

$
0
0

የ12ኛ ክፍል ፈተና ጉዳይ !

13614990_1080333545391634_3154661566058727962_nየፈተናው መሰረቅ ተከትሎ መንግስ የራስ መተማመን መንፈሱ የተሸመደመደ ሲሆን ኣሁንም ፈተናው ዳግመኛ ላለመሰረቁ ምንም መተማመኛ ነገር የለም።

የትግራይ ትምህርት ቢሮ “የ12ኛ ክፍል ፈተና ፈታኞች የህወሓት ኣባሎች ኣስተማሪዎች ብቻ መሆን ኣለባቸው” የሚል ጭንቀት የወለደው መላ ኣውጥቶ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ያሉ ወረዳዎች ምልመላ ለማካሄ ጥረት ኣድርጎዋል። በተለይ በእንደርታና የሳምረ ሰሓርቲ ወረዳ ኣስተማሪዎች ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል።

በመቐለ ኣፄ ዮውሃንስ ፬ ፕሪፓራቶሪ ትምህርት ቤትም ከደቡብ ምስራቅ የኣስተማሪዎች ተቃውሞ በመነሳት የህወሓት ኣባላት ያልሆኑና በኣይነ ቁራኛ የሚታዩ እምነት ያልተጣለባቸው የህወሓት ኣባላትም በደፈናው “ተቀንሳቹሃል” ተብለዋል።

* ድሮ በማትሪክ ፈተና የሚጨናነቀው ተፈታኝ ተማሪዎችና ወላጆቻቸው ብቻ ነበሩ። በኣሁኑ ሰዓት ግን ከተፈታኝ ይልቅ ፈታኙ መንግስ ኣጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ ይገኛል።

መንግስት 12ኛ ፈተና ከስርቆት ለመታደግ መላ ጠፍቶት ተቸግሮ ይገኛል።

Amdom Gebreslasie

ትዝብት! ….በዚህምኮ መንገድ አለ! (አስፋ ጫቦ)

$
0
0
አቶ አሰፋ ጫቦ

አቶ አሰፋ ጫቦ


አስፋ ጫቦ Dallas Texas USA

መንደርደሪያ

የዚህ ጽሁፍ ዋና አላማ በሚያዝያ ወር 2008 በዋሺንግቶን ዲሲ (Washington,D.C)  አከባቢ የ ት ዝ ፈ ለ ግ መጽሐፌን ለማስመረቅ በተዘጋጁት ሁለት መድረኮች የታዘብኩትን ለማካፈል ነው::

alem1ከሚያዚያ 14 እስከ ሚያዚዝያ 24,2008 Washington,D.C  አካባቢ በተለይም ሲልቨር ስፕሪንግ (Silver Spring) ሰነበትኩ። የጉዞዬ ዋና ምክንያት የ ት ፈ ለ ግ የተባለ የስብስብ ስራዬ ወደ መጽሐፍነት ስለተሸጋገረ አደባባይ ለማውጣት ነበር። ማስመርቅ ልንልም የምንችል ይመስለኛል። እዚህ አሜሪካ Book Signing Event ይሉታል።

ሁለት ወዳጆቼ መድረኩን አዘጋጁት። ሚያዝያ 16, 2008 አርታ አሌ ሆቴል ያሬድ ጥበቡ ወዳጆቹን ጋብዞ ያዘጋጀው ነበር። ሌሌዉ ሚያዝያ 21 2008 ታዋቂዋና የማከብራት ዓለም ፀሐይ ወዳጆ ያዘጋጀችው ነው።

ያሬድ ያዘጋጀው መድረክ ላይ ቡዙ ገጠመኞችም ነበሩ። የሆቴሉ ስም ራሱ፤አርታ አሌ ሆቴል፤  ለኔ ታሪካዊ ነው:: ከአፋር መሬት ከርሰ-ምድር የሚንተከተከው እሳተ ጎሞራ ስፍራ ስም ነው።የጓደኛዬ ልጅ፤ዶሊ፤ሀች-አምና ጎብኝታው ያነሳችውንና የተነሳችበትን ምስል Facebook ላይ ለጥፋ አየሁት:: ፈረንጅ ጎብኝዎች የለጠፉትን ከማየት በላይ አላጤንኩትም ነበር።ከኔ (ከኛ?) ይበልጥ ፈረንጅ ያውቀዋል እንደማለት ይመስለኛል።እዚህ አሜሪካ ታዲያ የሆቴል ስም ሆኖ ብቀ አለ::

yearedአራት በር ያለው ዘመናይ ምግብ ቤት ነው። ይበልጥ የገረመኝ ባለቤቱ፤ዶክተር ሰለሞን፤ ሐኪም ነው።ስለደነቀኝም ምክንያት ፈልጌ ደጋግሜ አነጋገርኩት።አለባባሱ፣አነጋገሩ፤የቃላቶቹና ሐሳቦቹም ምርጫ ፤አገለለጹ (Body Language) ጭምር የአሜሪካን ዘመናይ ኩባንያ ሥራ አስኪያጅ አይነት ሆነብኝ። ለመሆኑ ስንቶቻችን እንሆን ተፈጥሮ በለገሰን ስጦታ ሳንሰማራ ቀርተን እንዲህ ጓደኛ ወይም የሰፈራችን ልጆች በሔዱበት ፈለግ የተከተልነው? አሰኜኝ። በኔና  በዶክተር ሰለሞን ዘመን ዝንባሌህ/ተሰጥኦህ እንዲህ ነውና የህንን ወይም ያኛውን ብታጠናው/ብትማረው ይሻላል የሚል አልነበረም። የአሁንን አላውቀውምና የምለው ብዙም የለኝም።


የአሁን ትምህርት ትንሽ በፍንጭ ብቻ እንደማገኘውና እንደምሰማው  ምኑም ምኑም የሚጥም አልመስለኝም።ከሹሞቻችን የአንዳንዶቹ ያልላመ ሽርከት ትምህርት ከወፍጮ ቤት (Degree Mills) የመጣ ነው እየተባለ አበበ ገላውና ሌሎችም በሰነድ የተደገፈ ማስረጃ ሲያቀርቡም አያለህ።”ከመጠምጠም መማር ይቅደም!” (እዚህ ከመሿሿም በፊት ልንለው እንችላለን) የሚባለው ለዚህ ይስለኛል። ቾኩሎ አጉል ይጠመጥምና “ገብርኤል ፈጣሪዬ!” ሲል እጅ ከፍንጅ ይያዛል:: እዚያ ሌላ ምክንያት ፈልጌ ሌላ ቀን ብመልስበት የሚሻል ይመስለኛል።

አንድ ልረሳው የነበረው ነገር!! በስራ ምክንያት ከመሔዱ በስተቀር ዶክተር ሰለሞን አፋር አይደለም።ይህ ደሞ በመጠኑም ቢሆን ሰፋ ያለ ስዕል መሳል የመቻልን አዝማሚያ የሚጠቁም ይመስለኛል።በተለይም ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ የሆቴሉ፤የንግድ ድርጀቱ፤የመንግስት መስሪያ ቤት ስሞች፤በተለየም የኢትዮጵያ ፓሊስና ወታደር ማዕረግ ከኢትዮጵያ ተፋቶ የእንግሊዝና የአሜሪካ ስም በሆነበት ዘመን መሆኑ የበለጠ ክብደት የሚሰጠው ይመስለኛል።

ት ዝ ብ  ቱ

assefa1መጽሐፉ ምረቃ ላይ ንግግር፣መግለጫ ልንለውም የምንችል ይመስለኛል፤አደረኩ። መጽሐፉ ስብስብና 28 ምእራፎች አሉት። ዝርዝሩ ውስጥ አለገባሁም። አብነት ይኖራቸዋል ያልኩትን ጥቂቶች አነሳሁ።ከዚያ በፊት ግን መጽሐፉ የተዘርጋበበት ንፍቀ-ክበበ፤ትልቅ ምስል፤(Vista,Big Picture) ለማሳየት ሞከርኩ። መጽሐፉ ውስጥ ያሉት ምናልባት ካንድ ሁለት በስተቀር መድረኳ ኢትዮጵያ ነች። ስለዚህ ከኢትዮጵያ፣ማለትም ከኢትዮጵያ ታሪክ ጋር አዛምጄ ለማቅረብ ሞከርኩ።በዚህ አጭር ጊዜ፤በዚች በአንድ መጽሐፍ ሰበብ የኢትዮጵያን ታሪክ መዳሰስ እኔም ሆንኩ ማንም ሊያደርገው የሚችል አይመስለኝም። የኢትዮጵያን ህዝቦች ታሪክ ትልቁን ምስል በዚህ በተነሳው ጉዳይ ዙሪያ ለመሳል ሙከራ ነበር። ቢቻል ታሪኳን የምናይበት ሰፋ ያለ ትልቅ መንጽር ለመስራት ሙከራ መሆኑ ነው።

እዚህ ላይ አንድ የግርጌ ማስታወሻ (foot note) የሚሉትን አይነት ነገር ማለት እፈልጋለሁ። የኢትዮጵያ ታሪክ ስል እኔ ታሪክ ነው የምለውን አይደለም። በተቻለ መጠን ተጽፎ፤ተመዝግቦ፤ዛሬ ምድሪቱ ላይ ባሉት ሕዝቦችዋ ላይ የሚነጸባረቀውን እውነት ነው።ሕዝቦችዋ ደግሞ የብዙ ዘመናት አነባበሮ ናቸው:።ግምቴናምኞቴን አይደለም። ለፖለቲካ ፋይዳ ተብሎበግምት፣ተጣሞም፣ተንሸዋሮም ሲቀረብ አይና ወይ ይደነቀኛል፤አንዳንዴ ያስደነግጠኛል። መጽናኛዬ ግን “ይኸ ሀላፊና ረጋፊ ስለሆነ ትግስትና ጊዜም ስጠው!” የሚለው ነው። አጋጣሚው ሲገኝ ደግሞ አውራ ጎዳናው በዚህ በኩል ነው ብዬ ከመጠቆምም ወደኋላ አልልም።ወደኋላ አለማለት ነው!! ሆኖም  ያኛው ወገን የሚለው ውስጥምኮ አንዳንድ እውነት አይጠፋም ማለቱ ጥሩ ነው። በር አለመዝጋት!አለመቀርቀር! ለማለት ነው። የእውነቱ ብቸኛ ባሌቤት (Monopoly) ያለው የለም!

assefa12ሁለቱም አውዶች ላይ በአካል ቋንቋ (Body Language) ሆነ በቃላት የተገለጠው ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ነበር ለማለት የምችል ይመስለኛል::በጥሞናና በተመስጦ የማዳመጥ ነገር በእያንዳንዱ ፊት አያለሁ::አነባለህ! ቆሜስለምናገር፤ተቀመጠው ስለሚያዳምጡ፣ ለማስታዋል ከሁሉም የተሻለ እድል ነበረኝ። በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ ኦርቶዶክሶቹ “አልዕሉ አልባቢክሙ ሀበ እግዚአብሔር….” የሚሉት አለ።ልቡናችህን አንቅታችህ/አንግሳችህ አድምጡ ለማለት ይመስለኛል። ያንን ያየሁ ይመስለኛል!

ጣይቱ ማእከል የማደርገውን ገለጻ ጨርሼ ቁጭ ስል አጠገቤ የነበረው አያሌው ከበደ “ጋሽ አስፋ ሰውኮ ቆሞ ያጨብጭባል!” ሲለኝ አፍሬና ደንግጬ ተነሳህ። ፈርንጆቹ Standing Oviation የሚሉት ነው።ከዚያም ወደጥያቄና መልስ ወይ፤ወደ አስተያየት መስጠት ተኬደ።

በጥያቄና መልሱ ወቅት ሁለት ነገሮች/ ነጥቦች ጎልተው የወጡ ይመስለኛል። አንደኛው፤ ከጥያቄ ይልቅ የአስተያየቱ አይነነት ተቀራራቢነት ነበረ።”…ዛሬ የነገረከኝ አዲስ ነገር የለዉም!ያው የማውቀውን ወይም አውቃለሁ የምለውን የአገሬን ታሪክ ነው። አንተ፤እንዲህ አቀራርበህ፤ፈተህ፣አቃለህ ተርጉመህ ስትነገርኝ እንዴት አባቴ ሆኜ ነው እኔ እንዲህ ሳላይ የቀረሁት!” የሚል ነው። ቃል በቃልም ባይሆን መንፈሱ የኸው ነበር።እንዲያ ተከፍቶ ሳይታይ በባከነ ጊዜ/ ዘመን መቆጨትያለበት መስሎ ታየኝ።ሁለተኛው ክፍልደግሞ “ነገም ይነጋል!መንገድም፣ አማራጭ መንገድም  ሞልቷል። ያንን የመፈለግ እንጅ አለቀ-ደቀቀ የሚያሰኝ ነገር የለም!” የሚል ነበር። በተስፋና በይቻላል መልክ መመልከት ልንለው የምንችል ይመስለኛል። Posetive Thinking የሚሉት። “ጥሩ ተመኝ ጥሩ እንድታገኝ”እንዲሉ።

የሰው ስብጥር ራሱ ገረመኝ። በእድሜ ከ50 በላይ የምንሆነው እኔን ጨምሮ 10% ብንሆን ነው። በአብዛኛው ምሁር፤ሊቀ ሊቃውንት ሊባል የሚችለው ስብጥር መስለኝ።ይህን ያውቅኩት ያሬድ ጥበቡ ያዘጋጀው መድረክ ላይ ነበር:: መጽሐፉን ለገዙት ፊርማና ትንሽ አስተያየት መጻፍ እንደጀመርኩ  ነበር። “ለአቶ” ብዬ ስጀመር ያሬድ ” አሴ! ምን ነካህ? እሱኮ ዶከተር ነው !”አንድ ሁለቴ ሲለኝ  “ማእረግህን ምን ልበል?” ማለት ጀመርኩ። እንደገመትኩትኩት አንድ አስሩ ያክል በየመስካቸው ዶክቶሮች ነበሩ።

ሌላው የማውቀው የሚያውቀኝ ብዙ ሰው አገኘሁ። ማእከላዊ የማውቀውን ምስማኩ አስራትንና መስፍን ቡልቻን አገኘሁት። መስፍንን ረስቼው ኖሮ ደጋግሞ “ጋሽ አስፋ ምን ነካህ ?!መስፍን ቡልቻኮ ነኝ!” አለኝ። ለካስ አንዴ የጻፍኩት መጻጽፍ ላይ መስፍን ቡልቻንና ሳምሶን ሙላትን አንስቼ ነበር። ቀና ብሩህ የመርካቶ ንጋዴ ልጆች ነበሩ። ሳምሶንን የዛሬ ስንትስ አመት  Cambridge, Massachussettes  አገኘሁት። የኮከበ ጽባህ ልጆችን ከኔ ቀደም ሲል የነበረውን ኢሳይያስንም ጭምር አገኘሁት። አንድ የአርባ ምንጭ ልጅም አገኘሁትና “ስለ አርባምንጭ አልጻፍኩም ይቅርታ ስለጋሞና ስለጨንቻ ጽፌአለሁና በዚያ ተካካስ!” አልኩት።

ጣይቱ ማእከል ሌላው የደነቀኝ፤በተለምዶ በየወሩ የግጥም ንባብ አለና የዚያን ማታ የተነበበው ነበር። ገጣሚዎቹች ወጣት ልጆች ነበሩ። ግጥማቸው ምራቁን አጣጥሞ የዋጠ፤ክንፍ ያለው፤ወደላይ ወደሕዋው የነጠቀ ፤የመጎርጎር፤ እግር ያለው፤ ስንጥሮ ወደ እመቀ እመቃት ወርዶ ጉዳችንንና ለእልናችንን የሚያበስር ነበር።

ከሁሉም በላይ የጀነራል መርዕድ ንጉሴን ልጆች አስተዋይንና እህቱን አገኘኋቸህ። አስተዋይ መርዕድ ከኔ ጋር ማእከላዊእ፣ታች ግቢ፣7 ቁጥር፤ ጨለማ ቤት አብሮኝ ታስሮ ነበር። የትዝታ ፈለግ ከተዘከረላቸው ሰዎች አንዱ ጀነራል መርድ ንጉሴ ነበሩትንሽ ተላቀስን!! የልባችን ሳይደርስ በሰው ብዛት ተለያየን።የእለቱ ሙሽራ አየነትም ስለነበርኩ ያንንም ይሕንንም ሳነጋገር በቂ ጊዜ አለነበረኝም። ለዚያውም ከአደራሹ ሰአት እላፊ ደርሷልና ውጡ ተበለን ነበር የተለያየነው።

ያንለት ማታ ኩኩ ሰብስቤም አገኘኋት። በዝና እንጅ አንተዋወቅም። የመጣሁ ሰሞን ወንድምዋ DC ምን የመስለ ምሳ ፖቶማክ (Potomac) ወንዝ ዳርቻ ጋብዞኝ ነበር። ኩኩን በቅርበት የተዋወውኩት ራት ላይ ነበር።

ራት-ምሳ ግብዣ እንደልብ ነበር። 10ሩን ቀን መኝታዬ ጋ የምደረሰው ሁሌም ከዘጠኝ ሰአት በኋላ ነበር። አንዱን ምሸት፤ በማላውቀው ከተማ፤ዝናብ እየጣለ፤በማላውቃት፤በማታውቀኝ ሴት መሪነት (GPS) ወደቤት ሲሐድ ፖሊስ አስቆመኝ።መኪናዬ (የተከራየሁት) የተሰመረለትን ስቶ ሳይዋዥቅ የቀረ አይመስለኝም: እነደተለመደው መንጃ ፈቃድ ጠይቆኝ “ስትጠጣ ነበር?!” አለኝ። “አዎን!” አለኩት “ምን?!” ሲለኝ “ውሐ!” አለኩት። እውነቴን ነበር። ያን ያህል የምውደው ዊስኪ Johny Walker ጭመር ጣእሙ ጠፍቶብኝ መጠጣት ካቆመኩ ዘመን የለውም። ፖሊሱ ታዲያ ጢም ብሎ ሰክሮ የንገዳገዳል።ጨንቻ “ድንቄም! ዋሪቴም! ዋኬኔም!” የምሉትን አስታወሰኝ። ዋሪቴ ማን እንደሆነች አላውቅም። ወደዶርዜ መሔጃው ላይ፤ከመሪጌታ ብቃለ ከበበው ቤት ዝቅ በሎ፣ጋሽ ጣሴ ዋኬኔ እነደነበረ አውቃለሁ። “ድንቄም ሕግ ማስከበር!” ለማለት ነው።

ብቻ ራት ለመብላት ሔድንና ኩኩም መጣች።”አንተ ከበዛ ወርቅ አስፋው በስተቀረ ለመሆኑ ሌላ አርቲስት ታውቃለህ?” ብላ ጀመረች። የበዛወርቅን የ ት ዝ  “እስላም ክርሲቲያኑን እንዲህ ያዋሐደው፤ማቱቡ  ነውከጥንት አብሮ የገመደው!”የሚለውን ደጋግሜ አንስቸው ኖሯል።” የአንችንም ዘፈን በጣም እወደዋለሁ!” አልኳት። “መች በአደባባይ መሰከረክ!?” አለችኝ። “እንዲያውም ከአርቲሲስቶቹ ሁሉ የምትቀረብኝ አንች ነሽ!” አልኳት። “ለምን?” ብትለኝ “አንቺም እኔም የጨንቻ ልጆች ነንና!” አለኳት። አባትዋ፤ደጃዝማች ስበስቤ ሽብሩ፤እኔ ልጅ ሳለሁ የጋሞ ጉፋ ጠቅላይ ግዛት እንደራሴ ነበሩና አንድ ክረምት ልጆቻቸው ጭምር መጥተው ማየቴን ነገርኳት። ተማመንና ሁለትየጨንቻ ልጆች ተባብለን ተዛመድን። ኩኩ ሰብስቤ፤የተናናች፣እንደልብዋ የምትናገር፣የምትጫወት፣የምትጫወተውን የምታውቅ(small Talk)፣ነጻ የሚሏት አይነት (Cosmopolitan) አርስቲስት ሁና አገኘኋት።አነጎራጎረችልንም!

ቀኑ አርብ ምሸት፤የኦርቶዶክሶቹ ስቅለት ለት ነበር። የገረመኝ አንድ እኔ ያለሁበት ማእድ ሲቀረ የተረፈው የጾም ራት ነበር።ያልጠበኩት ስለነበር ገረመኝ። ከዚህ ትምህርቱ፤ለኔ፤ሌላውን በራሳችን መመዘኛ ብቻ አለመለካቱ ጥሩ መሆኑን ነበር።

ሌላ ከእለቱ ቅኝት፤ማለትም ከመጽሐፉ መረቃ ጋር የማይሔድም ገጥሞኝ ነበር። ያንን የመጨረሻው ጠያቂ ሆኖ የመጣው በዕዉቀቱ ሥዩም ነበር። “ኢ.ጭ.አ.ት(የኢትዮጵያ ጭቁኖች አብዮታዊ ትግል) የሚባል የደርግ ዘመን የፖለቲካ ድርጀት ሊቀ መንበር ነበርክና ስለዚያ አስርዳን” አለ። አንድምታዉ “ጠባብ ብሔርተኛ ሆነህ ደግሞ ስለኢትዮጵያ ታወራለህ!” እንደማለት መሰለኝ።

መጀመሪያ የመጣለኝ Non Sequitur[1] ነው። Non Sequitur ማለት” ይህ ከዚያኛውአይከተልም!” እንደማለት ነው። የህግ ባለሙያን ነኝ።በዚህም ላይ ዩንቨርስቲ የመጀመሪያ አመት ይሁን ሁለተኛ ተማሪ ሳለሁ  ፈልስፍና 101 የሚባለውንም ወስጃለሁ። ይህ 101 ደግሞ ሎጂክ (Logic) የሚሉት ነው። በዕውቀቱ ደግሞ ዩኒቨርስቲም ተምሯል። ያ 101 አሁን መኖር አለመኖሩን አላውቅም። ብቻ ሰለኢ.ጭ.አ.ት አስረዳሁ! “ለመሆኑ ከዚህ ጋር እንዴትአገናኜኸው?”አላልኩም። ያተገቢው መልስ የነበር ይመስለኛል ።

በእውቀቱን አምና ዲስ የሔድኩ ጊዜ ከሌሎች “ጋሽ አስፋ ያንተን ጽሁፍ እያነበብን ነው ያደግነው!” ከሚሉት ብዙ ወጣት ምሁራን ጋር አግንቼው ነበር። እንዲያውም ያንተ ጽሁፍ ስበስብ በሙሉ አለኝ ብሎኝ ይህ መጽሐፍ የማድረጉ ሀሳብ የመነጨው ከበውቀቱ ነበር። ኢትዮጵያ ሲመለስ እንዲተባበሩት የልጄንና የእህቴንም ስልክ ቁጥር ሰጠሁት። ከዚያ በFacebookና በemail ብለው- ብለው  ጠፋ! ጠፋ! የሰጠኝ ስልክ አንዴ ስደውል አንድ ሰው ጸያፍ መልስ ሰጠኝና ተውኩት።አሁን እነደገና አሜሪካ መጣ ሲሉ ጊዜ ስልክ ቁጥሩን ፈልጌ ስደውል ዘጋብኝ። ለካ መጽሀፍ ሊያሳትም ኖሯል።

አሁን ሳየው ለካ በዕውቀቱ እኔ “ማነው ነፍጠኛ ?”በሚል የጻፍኩትንና በቃለ መጠይቅም የሰጠሁትን ቃል በቃል ጠቅሶ ለአጼ ምንሊክ መልሶ ማቋቋሚያ (Rehabilitation) በሚመስል ተጠቀመበት። መጀመርያ፤ነገር የኔ “ማነው ነፍጠኛ?”መንፈስ ማንንም መልሶ ለማቋቋም ሳይሆን ታሪክ በተገቢ መልኩ እንዲታይ ነበር። ምንሊክም ሆነ ማንም እውነተኛና ታሪክ ነጋሪ እንጅ መልሶ ማቋቋምን የሚፈልጉ አይመስለኝም።በዚህ ላይ ከእገሌ ውሰደኩ ማለት ስነምግባር ብቻ ሳይሆን ሕግም ነው። እኔ ሕግ ትምህርት ቤት የዚህ ፕላጄሪሲም(Plagerisim) የሚባለው ለ4 አመት ዳኛ ነበርኩ። “ከእገሌ ወሰደኩ” ሳይል ፤የግርጌ ማስተዋወሻ (footnote)ሳይለጥፍ የሚጽፍ ተማሪ ለመቅጣታት የተቋቋመ Honer Court ይባል ነበር።

ይህ ደግሞ ሌላ አስታውሰኝ። የት ዝ ታ ፈለግ ውስጥ የኔይቱ ጀገና የሚል ስለዘውዲቱ አስማረ የተጻፈ አለ። አንድ ሌላ ሰው ደግሞ “የኔ ጀግና!” በሚል መጽሀፍ ጽፏል ተባልኩና ያ መጽሐፍ ስሞኑን ሊመጣልኝ ነው።”ከአሰፋ አገኘሁ” አይልም ። ሕጉ ይቅርና ከእገሌ ውሰድኩ ነውርነት የለውም። ወጥ ሐሳብ ያለን ጥቂቶች ነን።አብዛኛዎቻችን ሌላው ከተናገረውና  ከጻፈው እያዳብረን ነው።

በዕውቀቱ ሥዩም የትና የት ሊደርስ የሚችል ጸሐፊ፤ከሁሉም በላይ ገጣሚ ነው። ግጥሞቹ፤ቢያንስ እኔ ያነበብኳቸው፣የመጠቁና ፍልስፍና የሚሞክራቸው ናቸው። በእውቀቱ እንዲባክንብን አልፈልግም። ተስፋዬ ገብረአብ ምን የመስለ፤የትና የት ይድርሳል ያልኩት ደራሲ ባከነበን። አልባሌ፤አላፊ ጠፊ፤ ፖለቲካ ውስጥ ገብቶ የባከነብን ይመስለኛል።ለዚህ መድኅኒቱ ለጥበቡና ለራስ ታማኝ መሆን ነው።ለነዚህ ታመኝ የሆነ ዝንተ አለም ታማኝ ሁኖ ይኖራል።

ትምሕርቱ

እኔ ከዚህ መጽሐፍ ምርቃ ዘላቂ ትምህርት ያገኘሁ ይመስለኛል።ነገር ዓለሙ ሁሉ ሰበብ-አስባብ ይፈልጋል ልንልም የምንችል ይመስለኛል። በዚህ በሳይንሱ ክሪቲካል ማስ (Critical Mass)የሚሉት አይነት መሆኑ ነው። “ሰኔና ሰኞ!” ሲገናኝ እንደማለት ነው ። በክርቲካል ማስ ወሐ ሲፈላ ይተናል። ሲቀዘቅዝ ደግሞ ወደበርዶነት ይለወጣል። ያንን ሲያሞቁት ወይም ሲያቀዘቅዙት ደግሞ ውሀ ይሆናል። የኔ አንዲት ስብስብ መጽሐፍ ያንን ያክል” ሰኔና ሰኞ “ሆናለች ለማለት አይደለም። ለማለት የፈለኩት አንዳች ነገር ሊሆን ወይም ላይሆን ሰበብ አስባብ ይፈለጋል ለማለት ነው። ከዚህም ተነስቼ የ ት ዝ ታ ፈ ለ ግ ሰበብ አስባቡ ሆና ያው ውስጣችን የታመቀንና ሊወጣ ምክንያት ሲሻ የነበረውን አውጣችው ወይም ለመውጣቱ ምክንያት ሆነች ለማለት ነው።

ለዚህ እስቲ ሁለት አባባሎችን እንውስደ። አንደኛው “ጠርጥር ገንነፎም ውስጥ አይጠፋም ስንጥር”ና  ሌላው “ቸር ተመኝ ቸር እንድታገኝ!” የሚሉትን። ይህንን በዘመናይ ቋንቋ Negative versus Posetive thinking ብለን ልናይ እንችላለን። ነገርን በቀና መንፈስና አጣሞ በመትርጎም ውስጥ ያለ ልዩነት መሆኑ ነው።

በዚህ “ገንፎም ውስጥ አይጠፋም ስንጥር!” ላይ June 26,2016 አንድ በኔ ላይ  የደረስ ምሳሌ ልስጥ።አንድ ሰው፤እዚህ ስሙን መጥራት የማልፈለገው፤ Facebook ላይ “ወዳጅ ልሁን “ብሎ ጠይቆኝ “እንኳን ደህና መጣህ!” ብዬ ተቀበልኩት። ቀጥሎ “ጤንነትህ?” ሲለኝ “እዚህ አሁን በጋና ወበቅም አለው” አልኩኝ። “ለመሆኑ የት ነው ያለኸው?” አለኝ.” Dallas Texas USA” አልኩት። “አሜሪካ ነው?” አለኝ::”.USA አሜሪካ ማለት ነው” አልኩኝ። “USA አሜሪካ መሆኑን ከአንተ በፊት አውቃለሁ!” አለኝ። በኔ ግምት ይህ “ገንፎ ውስጥ አይጠፋም ስንጥር” ሳይሆን ገንፎው ውስጥ ስንጠር ጨምሮ “ይኸው ስንጥር አለበት!” ብሎ ማስረጃ ለማቅረብ እንደመሞከር ነው። አንዳንዱ የፖሊቲካ አስተያየት ሳዳምጠው የዚህ ጣእም/ ምሬት/ሬት ያለው ስለሆነ ይሰውረን ነው። እኔ ይህንን ግለሰብ ከውዳጆች አንባ ሰርዠው ተገላገልኩ። ይሰውረን ማለት ነው የሚበጀው።

ገልጠን ብናየው

ቸር ተመኝ ቸር እንድታገኝን ለማስረዳተ ከፍ ብዬ አንስቼ የነበረውን እዚህእንዳለ እደግመዋለሁ:-

እዚህ ላይ አንድ የግርጌ ማስታወሻ(footnote ) የሚሉትን አይነት ነገር ማለት እፈልጋለሁ። የኢትዮጵያ ታሪክ ስል እኔ  ታሪክ ነው የምለውን አይደለም። በተቻለ መጠን  ተጽፎ፤ተመዝግቦ፤ዛሬ ምድሪቱ ላይ ባሉት ሕዝቦችዋ ላይ የሚነጸባረቀውን እውነት ነው።ሕዝቦችዋ ደግሞ የብዙ ዘመናት አነባበሮ ናቸው:: ግምቴና ምኞቴን አይደለም። ለፖለቲካ ፋይዳ ተብሎ በግምት፣ተጣሞም ፣ተንሸዋሮም ሲቀረብ አይና ወይ ይደነቀኛል፤አንዳንዴ ያስደነግጠኛል። መጽናኛዬ ግን “ይኸ  ሀላፊና ረጋፊ ስለሆነ ትግስትና ጊዜም ስጠው!” የሚለው ነው። አጋጣሚው ሲገኝ ደግሞ አውራ ጎዳናው በዚህ በኩል ነው ብዬ ከመጠቆምም ወደኋላ አልልም።ወደኋላ አለማለት ነው!! ሆኖም  ያኛው ወገን የሚለው ውስጥምኮ አንዳንድ እውነት አይጠፋም ማለቱ ጥሩ ነው። በር አለመዝጋት!አለመቀርቀር! ለማለት ነው። የእውነቱ ብቸኛ ባሌቤት(Monopoly) ያለው የለም!

ዛሬ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ንግግር፣ንትርክ፣ጭቅጭቅ፣ዉዝግብ ውስጥ በአብዛኛው ይህንን የማየው ይመስለኛል። ጤነኛናውን በሽተኛ ነህ ብለው ነገሩት። ጉንፋን የያዘው፣በነጭ ሽንኩርት፤ በጦስኝ፤ግፋ ቢልም አስፕሪን ወስዶ እንዳይድን ካንሰር ይዞሐል አሉት።ካንስረ ደጎሞ ቀዶ ጥገናን የሚጠይቅ በሽታ ነው።ብአብዛኛው ቀሳፊ በሽታም ነው። ነገሩ ያለው መጀመሪያውን ታመሐል ያለው ሐኪም የህክምና፤የሕመም አይነት የመለየት፣የመቻል ባለሙያ አለመሆኑን የመረዳት ጉዳይ ነው። ግፋ ቢል የዚህ በዘር ከፋፍለህ ግዛው የቅርብ ምንጩ የሙሶሊኒ የጣሊያን የምስራቅ አፍሪቃ ግዛት (Africa Orientale Italiana መሆኑ የመረዳትና የማስረዳት ጉዳይ ነው። ጉንፋንና ካንሰርን ለይቶ የመረዳት ጉዳይ ነው።

ታዲያ በዚህ በየድህረገጹ በተለይም የአማራና ለኦሮሞ መብትና ግዴታ እንታገላለን የሚሉት የሚገርመው ክርክራቸውና አስተያይታቸው ከኢትዮጵያ የተፋታ መሆኑ ነው። ኦሮሞ ከራያና አዘቦ ጀምሮ ያሌለበት ክፍለ ሐገር የለም። ኦሮሞ በኢትዩጵያ በሕዝብ ቁጥር አንደኛው ነው።በምራጫ እንኳን ቢከድ አብላጫው ኦሮሞ ስለሆነ  የኦሮሞ መንግስት ነው የሚሆነው። ከዘመን መሣሳፍንት ጀምሮ፤ ልጅ እያሱን፣ንግስት ዘውዲቱን፤ኃይለ ሥላሴ፣ጀነራል ተፈሪ በንቲንና መንግስቱ ኃይለማርያምን ጨምሮ መሪዎቻችን ኦሮሞዎች ነበሩ።ከ108 የደርግ አባላቱ ውስጥ ግማሽ ያክሉ ኦሮሞዎች ነበሩ። ከወያኔ ወዲህ ደግሞ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንቶችና ዋና ከተማዋን አዲስ አበባን የሚያስተዳድሩት ከንቲባዎቹ ኦሮሞች ናቸው። ያም ሆኖ በክርክራቸው፤ሙግታቸው፤ጭቅጭቃቸው ውስጥ የኢትዮጵያን ስም አይጠሩም። ይህ እንዲህ ከፍተው ሲያዩት ግራ የሚያገባ ነው። ወይም አዲሱ የወያኔ ክትባት፤ ካንሰር ታመሐል የሚለው እውነቱን ፍቆታል ማለት ነው። ዛሬ የመንግስት መሪዎችም የኢትዮጵያን ስም አይጠሩም። “ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! የሚለውን የምሰማው የሸገርን 102.1 FM ራዲዮ ስከፍት ብቻ ነው።ሰንጥር ገንፎ ውስጥ ጨምሮ “ይኸውና!” ማለት መስሎ ይታየኛል።

ሌላው የፖለቲካ ሊቃውንት ነን የሚሉ ሁሉ ሲናገሩም ሲጽፉም የሚክድዱት የ17ቱን አመት የደርግ ታሪክ ነው። የማያከራክረው ግፉና ጭካኔው ላይ ያቶኩሩና ሌላውን ይክዱታል። ብዙዎች ደግሞ የራሳቸውን ጉድ ለመሸፈን ደርግን መሽሎኪያ ቀዳዳ (Escape Goat)ሲያደርጉት ይታያሉ።ደርግ የሰራቸው ዘለዓአለማዊና ታሪካዊ ድርግቶች አሉ።ኢትዮጵያን ሬፑብሊክ አድርጓል። በሐይማኖት እኩልነት የእስልምና ተከታዮችን በአላት ብሔራዊ በአል አድርጎታል።ብየካቲት 25,1967 የገጠር መሬት አዋጅ ሕዝቡን ፤በተለይም የደቡብ ኢትዮጵያን ህዝብ ከዘመናት ጢሰኝነት፤ገባርነት ገላግሏል። የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝብ ማለት ደግሞ አብዛኛው ኦሮሞ ማለት ነው።የካቲት 25,1967 የምኒልክን የአስገባሪነት ቀነበር ደመሰሰ(Null and Void) ማለት ነው:: እርግጥ የሚቀጥል የመብት ፤የነፃነት የብሔረሰብ ጥያቄዎች አሉ። ያንን የምንጀምረዎ ከባዶ፤ከዜሮ ሳይሆን ደርግ ባጎነጸፈን ድል ላይ ተመስርተን ነው። 17 አመት የኢዮጵያን፤ያንድ ሀገርን ታሪክ መካድ “አላየሁም! አልስማሁም!” ማለት ለፖለቲክ ንግድ ካልሆነ በስተቀር ፋይዳ ያለው አይመስለኝም።የጤናም አይመስለኝም!

ሕዝቡ ግን እውነቱን ያውቃል።አንድ ማስረጃ ልጥቀስ።ሶማሌ ኢትዮጵያን በወረረች ጊዜ ሚሊሽያ የሆነው የኢትዮጵያ ገበሬ “ተነስ!” ሲባል ራሱ ገንፍሎ፤ፈንቅሎ ነበር ከዳር እስከዳር የወጣው። ” ለዛሬ ይበቃልና ወደቤታቸሁ ተመለሱ!” ሲባሉ “አንመለስም!” ብለው ያለቀሱ እንደነበሩ የዐይን ምስክር ነበርኩኝ። ከዚህ አንዱ አርባምንጭ ላይ ከጎፋ አውራጃ፤ከባንካ ማስኬቶ ወረዳ የመጡ ሁለት እደሜያቸው 20 ውስጥ ይሆኑ ሴቶችን አርባ ምንጭ ላይ “ተመለሱ!!” አልኳቸው።ልንጓጉዘው ከምንችለው በላይ ስለመጣብንና ምናልባትም ሴቶችን ማስተናገጃ አልተዘጋጀም ይሆናል በሚል ግምትም ጭምር ነበር። አለቀሱ! “አስፋ አትዘምቱም ብሎናል!” ብለው የደርግ አባል ለነበረው በንጉሴ ወልዴ ላይ ከሰሱኝ። ዘመቱ! “ነጻ ያወጣንን አብዮት ጠላት አይቀምንም!” ነበር መልእክቱ:

ያለፈ ዘመን ቁስል፤ የሻረ ቁስል መርቁዟል ያሉ፤የአገራቸውን ስም በአደባባይ መጥራት ያልፈለጉ፤”የጋራ ቤታቸውን” የካዱ የት እንደደርሱ የትላንትናዋ ዩጎዝላቢያ፤የዛሬይቱ ብጥቅጣቂ ወይም ወደዚያ በማምራት ያልቸውን ሶሪያን ልብ ይሏል።ትምህርቱ  ከታሪክ መጽሐፍት ሳይሆን ፊት ለፊታችን ተገትሯል! ተውጥሯል! ተሰትሯል!

ሲጠቃለል

የትዝታ ፈለግ ከጠበኩት በላይና ውጭ ሔዶብኛል።ምን ጠብቀህ ነበር ብባል መልስ የለኝም።መጀመሪያ በመጽፍሐ መልክ መታተሙ ራሱ የኔ ሐሳብ አልነበረም።” የአንተን ጽሁፍ እያነበብን ነው ያደግነው” በሚሉ ወጣቶች አነሳኝነት ነበር።እዚህ አሜሪካ በምረቃው ላይ የሆነውን ለመግለጽ ሞክሪያለሁ።በስልክ፤ በFacebook, በemail በMessenger የደረሰኝ መልዕከት ቁጥር ስፍር ያለውም።መልእከቱ ከመላው አለም ነው ለማለት እችላለሁ።ከኢትዮጵያ፣ከጨንቻ ጀምሮ ደሴ፤ባህር ዳር ጎንደር፤መቀሌ ይገኙበታል።ይበልጥ የደነቀኝ የአቦቦነሽ አበራ ነው። አቦነሽ አሁን የተዘጋው የኢትዮጲ መጽሔት አባልና አዘጋጅም የነበረች ነች::Facebook ላይ ነው የተዋወቀነው።በስደት ናይሮቢ፤ኬኒያነውያለችው።መጽሐፉንይዛየተነሳችውንፎቶግራፍ ለጠፍችው።መልዕክቱ”መጽሐፉን በቁጥጥር ስር አዉለነዋል!” ይላል። በስልክ  “እንዴት አገኜሽው?” አልኳት። “ተከራይቼ ነው!” አለችኝ።

የት ዝ ታ ፈ ለ ግ ውስጥ  ሰዎች፤አነባቢዎቹ ምን አዩበት? ምን ታየበት? የሚል ጥያቄ ማንሳቱ ጥሩ ይመስለኛል። በኔ ግምት መጀመሪያ ነገር የት ዝ ታ ፈ ለ ግ ውስጥ የተወሳሰበ ነገር የለበትም። ይህም ማለት ሰው፤አንባቢው፣ያልተወሳሰበ ነገር ይወዳል ማለት ነው።ቀላሉን ነገር አወሳስበውው ለማቅረብ የሚሞክሩ ጸሐፊዎችም ተናጋሪዎችም አሉ። እርግጠኛ ምክንያታቸውም ባላውቀውም “ነገሩ እንዲህ እንደምታስቡት ቀላል እንዳይመስላችህ!” የሚል  አንድምታ ለማስተላለፍ ይመስለኛል። በዚያውም “እኔ ሆኜ ነው እንዲህ ያፍታታሁላችህ እንጂ እንዲህ ቀላል እንዳይመላችህ!” ለማለትም ጭምር ይመስለኛል። አውቂ ነኝም ለማለትና ከሌላው “ተራ ሰው” ተለይቶና ገንጥል ብሎ፣ጎልቶ፣ፍክቶ ለመታየትም ይመስለኛል።

በኔ አስተያየት የ ት ዝ ታ ፈ ለ ግ እሽጉን ከፍቶ ለማየት መሞከሩ ይመስለኛል ተነባቢነት ያስገኘለት።”ገልጠን ብናየው!” እንደማለት ነው። ወይም በአሉ ግርማ “መጋረጃው ተቀዶ መቅደሱ ታዬ!” እንዳለው መሆኑ ነው።በአጭሩ እሽጉን ከፍቶ፣ ሳጥኑ፣ፓኮው ውስጥ ምን ምን እንዳለ የመመርመር ጉዳይ ነው።መጀመሪያውኑ ሳጥኑን የቆለፈው፤እሽጉን ያሸገው አላዋቂም ሊሆን ይችላል ብሎ የመጠርጠር ጉዳይም ሊኖር ይችላል::ይገባልም!! አብሮ መታሸግ፤መቆለፍ ያሌለባቸው አብረው ከታሸጉ” አጥፊና ጠፊም!”ሊሆኑ ይችላሉ። በዚህም ላይ ለስንት ዘመንስ ይታሸጋል የሚሉትም አለ። ማንኛናውም እሽግ ዘመኑ ያልፍበትና(Expire Date) ካልታደስ ሊቃጠል ወይም ጎጅም ሊሆነ ይችላል። ከሁሉም በላይ እሽጉ ውስጥት የተበላሽ፤የበሰበሰ ፤ጠረኑን የለጠ፣ሊወገድ የሚገባውም ሊኖር ይችላል ብሎ መፈተሹ ጉዳት ያለበት አይመስለኝም።

ከዚህ ጋር የሚያያዝ እሽጉ እንዳይከፈትና ውስጡ እንዳይታይ የሚፈልጉ “የፖለቲካ ድርጅቶችና “የፖለቲካ “ጠበብቶች” ብዛት እነደ አሸን የፈላ ይመስለኛል።የተገነቡት መስረቱ የጠና መሠረት ላይ ስለአልሆነ፣የእምቧይ ካብ ወይም የተልባ ክምርነትም ሰስለማይጡ ነካ ሲያደርጉት መነሸራተቱ ስለማይቀር፣ይህንንም ስለሚያቁት “ዕውነት ለምኔ!”ይሆኑና “አትንገሩን! አትደርሱብን!”
የሚሉትም አላቸው። የፖለቲካ የንግድ ኩባናያ መሆኑ ነው።

የኢትዮጵያ ሕዝብ፤ ማንናቸውም ህዝብ፣ እውነቱ ሲነገረው ያውቃል። ራሱ ከሚያውቀውም ጋር ያነጣጥትርና “ይህ እውነት ነው!” ይላል። ያንን ካላለም “እውነት ይመስለኛል!”ይላል። ካልሆነ ደግሞ “አልገባኝም! ሆኖምአልጣመኝም!”ይላል።የትዝታ ፈለግ ይህንን መሠረታዊ ነገር ይጫረ ይመስለኛል።

ከሁሉም በላይ ግን ወዳጆቼ፤ዘመዶቼ፤ልጆቼ፤ከሁሉም በላይ የልጅ ልጆች ወደውታልና ከዚህ በላይ ጸጋ ያለ አይመስለኝ። እመቤት አስፋ እንደምትነገረኝ ልጆችዋ መጽሐፉን ታቀፈው ነው ያደሩት። የወንድሜ ልጅ፤ግርማ ሐብተ ገብርኤል ከአርባ ምንጭ “አሴ አለቀስኩ!” አለ።በኩራት መሆኑ ነው።

በኦርቶዶክሶቹ ሕማማት ሔጄ በፋሲካ ማግስት ሰኞ ወደመጣሁበት ተመልስኩ።የመጀመሪያው መድረክ ሕማማት ዋዜማ፤ሁለተኞናው አርብ የስቅለት ለት ነበር። ከሁለት ቀን በኋላ ትንሳዔ ሆነና ተፈሰከ! ፋሲካ ሆነ! “ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ!”እንዲሉ::የፋሲካ ምን የመስለ ምሳ የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮጋዜጠኛው አሉላ ቤት የህ ቀረሸ የማይባል ምሳ ተጋበዝኩ።

ትንሳኤም ተከበረ!!

የኢትዮጵያን ትንሳኤ እመኛለሁ!!

ኢትዮጵያ በነፃነትዋ  ለዘለዐለም ትኑር!!

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

[1] Non Sequitur | Definition of Non Sequitur by Merriam-Webstera statement that is not connected in a logical or clear way to anything said before it.

 

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>