Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

በዋሽንግተን ዲሲ የሽግግር ምክርቤቱ አመራርm ስብሰባ

$
0
0

ውድ ኢትዮጵያውያን፤

አገራችን ምን አይነት ምስቅልቅል ውስጥ እንደሆነች ለማንም ማስረዳት አስፈላጊ አይደለም። ከዚህም አልፎ ተዘጋጅተንና አቅደን ካልጠበቅነው መጭው ስርአት ተመሳሳይ ወይም ከዚህኛው የከፋ ይሆናል ብለን ሁላችንም እንሰጋለን። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሽግግር ምክር ቤት ይህንን የዝግጅት አስፈላጊነትን ጽንሰ ሀሳብ ለህዝብ በአንክሮ ካስገነዘበ ወዲህ ዛሬ ይህ አጀንዳ በተቃዋሚ ድርጅቶች፤ በተለያዩ ተቋማት እንዲሁም በመላው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ዘንድ የመወያያ ርእስ ሆኗል።

በመጭው እሁድ ሚያዝያ 5 (April 13, 2014) ባዘጋጀነው ስብሰባ የተለያዩ የማህብረሰባችን ተወካዮች በዚሁ አንገብጋቢ ጉዳይ ላይ ንግግር ያደርጋሉ ከህዝብም ጋር ይወያያሉ። ይህ ስብሰባ የተሳካ ለማድረግ በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ የሚገኙ ጓደኞችዎንና ዘመድ ወዳጆችዎን በመጋበዝና እራስዎም በመገኘት የድርሻዎን ያበርክቱ ዘንድ በትህትና እንጠይቃለን። ስለስብሰባው በይበልጥ ለማወቅ፤ ከዚህ ኢሜይል ጋር ተያያዥ ሆኖ የተላከውን በራሪ ወረቀት ይመልከቱ።

የሽግግር ምክርቤቱ አመራር

ENTC-flyer (1)


የኢትዮጵያ ሽግግር ምክር ቤቱ ኢፕሪል 13 ስብሰባን በተመለከተ (ከሚሊዮኖች አንዱ)

$
0
0

ከሚሊዮኖች አንዱ

comment_stage_5የአንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ንቅናቄ በሚል የጀመረው እንቅስቃሴ፣ በዉጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ድጋፍ እያገኘ መጥቷል። ኢትዮጵያዉያን በአካባቢያቸው ካሉ የአንድነት ድጋፍ ማህበራት ጋር በመሆን ከሚደግፉት በተጨማሪ፣ የተለያዩ ሲቪክ ማህበራት፣ በዉጭ አገር ያሉ የፖለቲካ ደርጅቶች እንዲሁም ግለሰቦች ሳይቀር፣ ጉዳዩ የአንድ ፓርቲ ብቻ ሳይሆን የሕዝብ ጉዳይ ነው፣ በሚል ከሚሊዮኖች አንዱ ነን እያሉ ነው።

ከነዚህ፣ አገር ቤት እየተደረገ ያለዉን እንቅስቃሴ ከሚደግፉ ድርጅቶች መካከል፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት አንዱ ነው።  ምክር ቤቱ የራሱ አላማና ግብ ይዞ እየተንቀሳቀስ ያለ ደርጅት ነው።

በኢትዮጵያ የሚደረገዉን ሰላማዊና ሕጋዊ እንቅስቃሴ ምክር ቤቱ እንደሚደግፍ ብዙ ግዜ አሳዉቋል። አገር ቤት የሚደረገዉን ትግል የምክር ቤቱ መሪዎችና አባላት  ያሳነሱበት፣ ያንቋሸሹበት፣ «አይሰራም፣ ጊዜ ማጥፋት ነው» በሚል በተዘዋዋሪ መንግስት ሕዝቡ ድጋፍ እንዳይሰጥ የሞከሩበት ጊዜ የለም። ይልቅስ ፣ የሽግግር ምክር ቤቱ፣ በዳያስፖራ ያለው የሚሊዮኖች ንቅናቄ ግብረ ኃይል ተወካዮችን ልኮ አብሮ የሚሰራ ከመሆኑም ባሻገር፣ በተለያዩ መግለጫዎቹ አገር ቤት ለሚደረገው ትግል ያለውን ሶሊዳሪቲ በገሃድ ያሳየ ድርጅት ነው።

ለምሳሌ ኦክቶብር ፣ 2013  የሽግግር ምክር ቤቱ «በኢትዮጵያ ዉስጥ የሚደረገዉን ትግል እንደግፋለን» በሚል ርእስ ያወጣዉን መግለጫ ማንበብ እንችላለን። መግለጫዉ «የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት ለነዚህ ቆራጥ የፖለቲካ ድርጅቶች በተለይም ለሰማያዊ ፓርቲና የአንድነት ድርጅት አመራርና አባላቶች፤ እንዲሁም በየእስር ቤት ተወርውረው ለሚገኙት የኢትዮጵያ የክፉ ቀን ደራሽ ጀግኖች የድርጅት መሪዎችና ጋዜጠኞች፤ ያለንን ከፍተኛ አድናቆት ከመግለጽ ባሻገር፤ ይህንን ግፈኛ ስርአት በህዝባዊ አመጽ መታገልና ማስወገድ የድርጅታችን መርህ ከመሆኑ አኳያ ሙሉ ድጋፋችንን የምንሰጥ መሆኑን እናረጋግጣለን» ሲል ነው፣  አገር ቤት ላሉት ታጋዮች ምክር ቤቱ አጋርነቱን የገለጸው።

ምክር ቤቱ የአንድነት ፓርቲም ሆነ ሌሎች ሰላማዊ በሆነ መንገድ ታግለው፣ በምርጫ አሸንፈዉ፣ በሕጉ መሰረት ሕገ መንግስቱን አሻሽለው፣ ለሁሉም ዜጎች እኩል የሆነች፣ አንዲት፣ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ብትመጣ ፣ እንደ ማንኛዉም አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የሚመኙትና የሚናፍቁት ነው። ለዚህም ነው ድጋፋቸዉን እየሰጡ ያሉት።

ነገር ግን ነገሮች እንደተጠበቁ ላይሄዱ ይችላሉ። «በአገራችን ኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ቀዉስ የበለጠ እየከረረ፣ ኢሕአዴግ እርሱ ባወጣዉ ሕግ አልገዛም ብሎ፣  ሕገ ወጥና አምባገነናዊ እርምጃዎች በመዉሰድ ፣ ወደ አላስፈላጊ ደረጃ ከተኬደ፣ በኢትዮጵያ አናርኪ እንዳይፈጠር፣ ከወዲሁ አማራጭ መፍትሄ  ማዘጋጀት ያስፈልጋል» ብለው  በሽግግር ምክር ቤቱ የሚንቀሳቀሱ ወገኖች ያምናሉ። አሁን በስልጣን ላይ ያሉት አምባገነኖች ኢትዮጵያ እንድትፈራርስ ፍላጎት ሊኖራቸው ይችላል የሚል እምነት በመኖሩም፣ ከወዲሁ በተለይም በዉጭ ያለውን ኃይል በማሰባሰብና ወደ አንድ በማምጣት፣ ተጠባባቂ PLAN  B ለማዘጋጃት እየሰሩ ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት የሚል ስያሜም ለራሳቸው የሰጡት በዚህ ምክንያት ነው። ስልጣን ለመጨበጥ ሳይሆን፣ ነገሮችን በፈራረሱበት ወቅት፣ የሽግግር መንግስት ተቋቁሞ አገራችን እንደ አገር የምትቀጥልበትን ሁኔታ ለማረጋገጥ።

አገር ቤት ያለዉ ትግል ተጨባጭ ዉጤት አምጥቶ፣ በኢሕአዴግ እና በተቃዋሚዎች መካከል መግባባት ተፈጥሮ፣ አሁን ያለው ሕገ መንግስት ተሻሽሎ፣  ነገሮች ሁላችንም እንደምንፈልገው ቢሄዱና የሽግግር መንግስት ምክር አላስፈላጊ ከመሆኑ የተነሳ ቢከስም፣ ሁላችንም የምንመኘው ነው። ነገር ግን ያ እስኪሆን፣ «ምናልባት» በሚል መጠንቀቁ አስተዋይነት ነው። ለዚህም ነዉ ጥረታቸው ሊደገፍና ሊበረታታ የሚገባው።

የሽግግር ምክር ቤቱ፣ የፊታችን ሚያዚያ 5 ቀን በዋሺንግተን ዲሲ ስብሰባ ያደርጋል። ስብሰባዉን  ላይቭ በፓልቶክ፣ ወይንም፣ ቴሌኮንፈራንስ የሚተላለፍ ከሆነ ለመከታተል እሞክራለሁ። በዲሲ አካባቢ ያሉ ኢትዮጵያዉያን በአካል ስብሰባዉን እንዲካፈሉ፣ ጥያቄዎችን እንዲጠይቁ፣ ሃሳባቸውን እንዲገልጹም አበረታታለሁ። በአገር ጉዳይ ላይ መመካከርና  መወያየት ምንጊዜም ጠቃሚ ነውና።

ስብሰባው፣ ብዙ ጊዜ በዳያስፖራ ከተለመደውና አሰልቺ ከሆነው፣ አገዛዙን ከማዉግዝና ከመስደብ ፖለቲካ ያለፈ፣ የተጨበጡና ሥራ ላይ ያተኮሩ፣ ኢትዮጵያዊያን ማሰባብስ የሚችሉ፣ በሰለጠነ መንፈስ የሚቀርቡ፣ አንኳር ቁም ነገሮችን ጉዳዮችን አንስቶ እንደሚወያይ ተስፋ አደርጋለሁ።

 

 

የድንበሩና የዐባይ ጉዳይ!! (አንተነህ ሽፈራው)

የሪያዱ ሚስጥራዊ ቦንድ ሽያጭ ከሸፈ!

$
0
0

ሐሙስ ጅዳ ላይ ያልቀናው ቦንድ ሽያጭ ትናንት ሪያድ ከተማም ከሽፏል።
የሁለቱም ከተሞች እቅድ መክሸፍ ምክንያት የሕወሐት ሰዎች ጉልበት የመጠቀም ስሕተት መሆኑ ያመሳስለዋል።ጅዳ ኮሚዩኒቲ አዳራሽ አቶ ከድር የሚባል የሕወሐት ሰው አንዲትን ስብሰባ የምትሳተፍ እህት በጥፊ መትቶ ሞባይሏን ለመንጠቅ ባደረገው ትንቅንቅ ስብሰባው ወደሁከት ተቀይሮ መበተኑ ይታወሳል።ሪያድ ስለሆነው ደግሞ እንከታተል ።
የትናንቱ የሪያድ ስብሰባ ለኤምባሲው ሩቅ ያልሆኑ ከየብሄሩ ሐያ ሰዎች በድምሩ አንድ መቶ ሃምሳ ሰዎች ብቻ በሚስጥር የተጠሩበት ነበር።መረጃው ለህዝብ ይፋ ከተደረገ በኋላ በርካታ ሰው ወደኮሚዩኒቲው አዳራሽ በማምራት ለመግባት ይጠይቃል።ከመግቢያ በር “የጥሪ ካርድ አምጡ” ይባላል ።”የለንም” ይላል ህዝብ።”ከየትኛው ብሔር ናችሁ?”ብለው በረኞች ሲጠይቁ “ኢትዮጵያውያን ነን።ጉዳዩ እንደዜጋ ይመለከተናል።”ይላሉ።
በዚህ ምልልስ መሐል አንድ ሰው ሞባይል ሲቀርፅ የሕወሐት አባል የሆነ ግለሰብ ይመታውና ሞባይሉን ሊነጥቀው ይሞክራል ።በር ላይ የተሰበሰበው ኢትዮጵያዊ የዚህ ሕወሐት እብሪት አበሳጭቶት ግብግብ ሲጀመር ከአዳራሹ ውስጥ የነበሩ ሌሎች ህወሀቶች መቀመጫ ወንበር በማንሳት የአዳራሹ መስተዋት በመሰባበር ህዝቡን ለመደብደብ ወደውጭ ይወጣሉ።
የኮሚዩኒቲው ፀጥታ አስከባሪ የሳዑዲ ፖሊሶች በመሐል ገብተው ነገሮች በቁጥጥር ስር ዋለ።የችግሩን መከሰት የሰሙት አምባሳደር መሐመድ ሐሰን መጀመርያ ላይ ፀብ ያጫረውን ሰው አምጡልኝ።የኤምባሲው ሰራተኛ ቢሆን እንኳ በህግ ይከሰሳል።”አሉ።ሰውየውን ህወሀቶች አስቀድመው ቢያሸሹትም በሕዝብ ጥቆማ ያሸሸው ሰው ይያዛል።አምባሳደሩ ሰውየው ህወሐት መሆኑን ሲያውቁ አፈገፈጉ።”በቃ ጉዳዩን ጸውስጥ እንጨርሰዋለን።አሁን ወደጉዳያችን እንግባ።”ብለው በግርግሩ ያለጥሪ ከገቡት ሰዎች ጭምር ስብሰባው ተጀመረ።
ገና እንደተጀመረ አንድ ሰው ብድግ ብሎ “ሀገራችን ውስጥ በሃይማኖታችን ምክንያት ቁምስቅል የምታሳዩን አንሶ በሰው ሐገር እንዴት ትደበድቡናላችሁ?”ብሎ እምባ እየተናነቀው ተናገረ!
ከበር ላይ የህወሓት እብሪተኞች የፈፀሙት የንቀት ድርጊት ከዚህ ሰው ንግግር ታክሎ የመንግሥት ደጋፊ የሚባሉ ሰዎችን ሳይቀር አስከፍቶ እያንዳንዱ ሰው ከወንበሩ ብድግ አዳራሹን ለቆ ወጣ!
ኢትዮጵያ የግል መኝታ ቤታቸው የምትመስላቸውና በሌላው ዜጋ የሐገር ባለቤትነት የማያምኑ ጭፍን የህወሓት ግልፍተኞች የሪያድና ጅዳን የህዳሴ ግድብ የልማት ውይይት(የቦንድ ሽያጭ) በዚህ መልኩ አኮላሽተውታል!!

Ethiopians in Jeddah, Saudi Arabia protest at government Officials

 

http://youtu.be/3JTy3tQvU2s

 

ስለፍትሕ ሲባል፤ ሥርዓቱ ይፍረስ! (ተመስገን ደሳለኝ)

$
0
0

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ (አዲስ አበባ)

Temesgen-Desalegn4ባለፉት አራት አስርታት ሀገሪቱ አያሌ ተግዳሮቶችን መጋፈጧ ባይዘነጋም፤ በተለያየ ጊዜ ሚሊዮኖችን ካረገፈው አሰቃቂው ረሃብ በማይተናነስ መልኩ ሕዝቦቿን ዋጋ ያስከፈለ ጉዳይ ቢኖር የፍትሕ አለመከበር ያስከተለው ሁለንተናዊ ምስቅልቅሎሽ ነው ብሎ ለመናገር የሚያስደፍሩ በርካታ ማሳያዎች አሉ።

የየካቲቱን አብዮት ጠልፎ ሥልጣኑን የተቆጣጠረው ወታደራዊው ደርግ፣ የፍርድ ቤት ደጆችን በጓጉንቸር ቆልፎ ሲያበቃ፣ የራሱ አባላት እጃቸውን እያወጡ ድምፅ በመስጠት በአፄው ባለስልጣናትንም ሆነ ግብረ-አበሮቹ በነበሩ መኮንኖች ላይ የሞት ቅጣትን ያህል የመጨረሻ ከባድ ውሳኔ የማሳለፍን አስደንጋጭ ክስተት ጨምሮ፤ ከከተማ እስከ ገጠር ያደራጃቸው የአብዮት ጠባቂዎችና የገበሬ ማሕበራት ከየቤቱ አንቀው እያወጡ “ነፃ እርምጃ” እንዲወስዱ፣ ከየእስር ቤቱ እየለቃቀሙ በጅምላ እንዲረሽኑ በአዋጅ የፈቀደበት ጊዜ የፍትሕ ምኩራቡ ፈርሶ በግላጭ የተቀበረበት ዕለት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። በርግጥ ይህ የማን-አለብኝነት አረመኔያዊ አገዛዝ የታቃውሞውን ጎራ በማጠናከር ታሪካዊ ውድቀቱ እንዲፋጠን ካደረጉ ምክንያቶች አንዱ እንደነበር ለመረዳት 17 ዓመታትን መውሰዱ አይዘነጋም።

“ፍትሕ አልባው አምባ-ገነናዊ የደርግ ስርዓት አማርሮ በርሃ ያስወጣንና ብሶት የወለደን የለውጥ ሃዋርያት ነን፤ በመቃብሩም ላይ ፍትሕ-ርትዕ የሰፈነባት ዲሞክራሲያዊት አገር እንመሰርታለ” በማለት ከበሮ ይደስቁ የነበሩት የያኔው “ነፃ አውጪዎች”ም፣ ደርግ አፍርሶ የቀበረውን የፍትሕ ምኩራብ አመዱን አራግፈው ቢያነሱትም፤ ባነበሩት አስመሳይ ሥርዓት በኩል በዘውግ ማንነት፣ በሙስናና በሙያ አልባ ዜጎች በክለው ክብር የለሽ ሲያደርጉት በጣት የሚቆጠሩ ወራት እንኳ አልፈጀባቸውም። ‹‹አዲስ ንጉስ አንጂ ለውጥ መቼ መጣ!›› እንዲል ከያኒው፤ ካስወገዱት የደርግ መንግስት ጋር ልዩነታቸው-ደርጉ ያልቻለበትን የተቃውሞ ድምፆች በአዋጅ እንዲንቀሳቀሱ በአንድ በኩል ፈቅደው፣ በሌላ በኩል መልሶ ለመጨፍለቅ የፍርድ ቤቶችን ባረኮት የመጠቀም ባለ ሁለት ገፅ ብልጠታቸው ብቻ ነው።

 

ይህ አይነቱ አገዛዝም ሥልጣን በያዘ ማግስት ሀገሪቱን እንዳሻው ለመርገጥ ሲቪል ቢሮክራሲውን ብቻ ሳይሆን የፍትሕ ስርዓቱንም በአምሳሉ አፍርሶ መስራት ነበረበት። ይሁንና ተቋሙን በዚህ መልኩ ለማዋቀር ጊዜ እንደሚያስፈልግ በመረዳቱ አሁን ድረስ በቂ መከራከሪያ ሊቀርብላቸው የማይችሉ ጉዳዮችን ከፍትሕ ሥርዓቱ ነጥቆ ሕገ-መንግስቱ ውስጥ በመዶል ለሌሎች ሰጥቷል። ለዚህ ደግሞ በቂ ማሳያ የሚሆነው፤ ሕገ-መንግስታዊነትን አስመልክቶ የሚነሱ የማጣራት ኃላፊነቶችን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት መስጠቱ ነው። በርግጥ አንዳንድ የወቅቱ ዘገባዎች እንደሚያሳዩት ሕገ-መንግስቱ በተረቀቀበት ሰሞን፣ ከሕገ-መንግስቱ የሚጣረሱ አዋጆች፣ ክሶች አሊያም ኩነቶች ሲፈጠሩ፣ የማጣራቱ ኃላፊነት የፍርድ ቤት መሆን አለበት ሲሉ የተከራከሩ ድምፆች ነበሩ። ዳሩ ውሎ-አድሮ ምን እንደሚሰሩ አስቀደመው የሚያውቁት ታጋዮች፣ በዛ ካድሬ-ዳኞች ባላፈሩበት ወቅት እንዳሻቸው ሕገ-መንግስቱን እየናዱ ቢያስሩ፣ አዋጅ ቢያወጡና ቢያስፈርዱ ድጋፉን የሚሰጣቸው ተቋም፣ በኢሠፓውያን እንደተሞላ የሚጠረጥሩት ፍርድ ቤት ሳይሆን፣ እንደ ልብ ሊቆጣጠሩት የሚችሉት የፌዴሬሽን ምክር ቤት መሆኑን በመረዳታቸው፣ በፓርላሜንታዊ ሥርዓት ትመራለች በተባለች ሀገር ብዙም ባልተለመደ አኳኋን ሕገ-መንግስታዊ ትርጉም የሚሻቸውን ጉዳዮች የማጣራት ስራን ለዚሁ ምክር ቤት ሰጡት፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎንም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የፍትሕ ተቋሙን በፓርቲ ፖለቲካ የተተበተበ፣ ለጉልበተኛ የሚገብር፣ ገንዘብ ሊገዛው የሚችል፣ ተቀናቃኝ ድምፆችን የማፈኛ መሳሪያ… አድርጎ የመቅረፅ ዓላማቸውን ማሳካት ችለዋል፡፡ በውጤቱም ተቋሙ የህግ የበላይነት የተደፈጠጠበት አድሎአዊና በየጊዜው ደካሞችን የሚያጠቃ ከሆነ እነሆ ከሁለት አስርት በላይ አስቆጥሯል።

 

የሆነው ሆኖ የሥርዓቱን ፍትሕ ረጋጭነት በተጨባጭ ፍፃሜዎች አስደግፎ ለማቅረብ ሁለት አብነቶችን እጠቅሳለሁ፡፡ ቀዳሚው የበርካታ ግፉአንን እሪታ ሲወክል፤ ተከታዩ ደግሞ የገዥዎቹን የሙስና እና የጓዳ ፖለቲካ ትስስሮች ይጠቁመናል ብዬ አምናለሁ።

 

የሞገስ ወልዱ-ጩኸት

ሰማይ ከመፍገጓ በፊት፣ ሁሌ ንጋት ላይ ኮተቤ አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ተነስቶ፣ በእግሩ ሰከም ሰከም እያለ ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት ግድም ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይደርስና ዋናው በር ፊት ለፊት ቆሞ ከአንድ ሰዓት ላላነሰ ጊዜ ‹‹ሌባ ዳኛ!›› እያለ ይጮኻል፡፡ ያፏጫል፡፡ ‹‹እናንተ ገላችሁኛል፤ ቀብራችሁኛል፤ አምላክ ፍርዱን ይሰጣል!›› በማለትም ተስፋው በሰማያዊው መንግስት ላይ ብቻ እንደሆነ ያውጃል፡፡ …ይህ ሰው እንደምን ያለ ከባድ በደል ቢደርስበት ይሆን ምሬቱ እንዲህ ጣራ የነካው?

 

አሳዛኙ የሞገስ ታሪክ እንዲህ ይጀምራል፡- በ1997 ዓ.ም የወላጅ እናቱን ወ/ሮ አስካለ ቢፋ ህልፈት ተከትሎ፣ ወንድሙ ኃይሉ ወልደአማኑኤል የወራሽነት ድርሻውን እንዲያካፍለው ክስ መስርቶ ሲያበቃ፤ ሶስት ጥያቄዎችን ለፍርድ ቤቱ ያቀርባል፡-

 

‹‹ንብረትነቱ የእናታችን የሆነ ቀበሌ 14/15 ውስጥ የሚገኝ 250 ካሬ ሜ. ላይ ያረፈ መኖሪያ ቤት፣ ሁለት ማሳ የእርሻ መሬት እና በንግድ ባንክ አራት ኪሎ ስላሴና መገናኛ ቅርንጫፍ የተቀመጠ መጠኑ ያልታወቀ ገንዘብን ያካፍለኝ፡፡››

 

የከሳሽ ወንድም የሆነው ኃይሉም ፍርድ ቤት ቀርቦ ‹‹ቤትም ሆነ የእርሻ መሬት የሚባል ነገር የለም፤ በባንክ አለ ስለሚባለው ገንዘብም አላውቅም፤ እናታችን በሞተችበት ወቅት ስሟን ለማስጠራት ስል የእርሷ የነበረውን መሬት በ30 ሺህ ብር ሸጬ፤ ለአርባ፣ ለመንፈቅ፣ ለተስካር 10 ሺህ ብር ያወጣሁ ሲሆን፤ ቀሪውን 20 ሺህ ደግሞ ለወንድሜ ማረፊያ የሚሆን ቤት ሰርቼበታለሁ›› ሲል ምላሽ ይሰጣል፡፡ ችሎቱም ‹ቤቱንና የእርሻ መሬቱን በተመለከተ የቀረበ ማስረጃ አለመኖሩን› ገልፆ ‹የ30 ሺህው ጉዳይ ግን ያለይግባኝ ባይ ፍቃድ ወጪ የተደረገ ስለሆነ፤ የገንዘቡ ግማሽ 15 ሺህ ብር ድርሻው ስለሆነ እንዲሰጠው› በማለት ወስኖ መዝገቡን ይዘጋል፡፡

 

በውሳኔው እጅግ በጣም የተበሳጨው ሞገስ፣ ጉዳዩን በይግባኝ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ይወስደዋል፤ ይግባኝ ሰሚውም ‹‹ቤቱ ይገኝበታል›› የተባለው ቀበሌ የእናታቸውን ማህደር እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ ግና፣ ሀገሪቷ ኢትዮጵያ ናትና፤ ቀበሌው ማህደሩ መጥፋቱን፣ ሟችም በተከሳሽ ቤት ይኖሩ እንደነበረ በደብዳቤ ያሳውቃል፡፡ ሆኖም ቀበሌው ይህንን ምላሽ ከሰጠ ከ14 ቀን በኋላ ‹የቀድሞውን አስተዳደር ጠይቄ ያገኘሁት መረጃ ነው› በማለት ለፍርድ ቤቱ እንዲህ የሚል ሌላ ደብዳቤ ይልካል፡- ‹ወ/ሮ አስካለ የግል መኖሪያ ቤት የነበራቸው ሲሆን፣ ቤቱ ያረፈበት መሬት ለ‹‹ሪል እስቴት›› በመሰጠቱ፤ ምትክ ቦታና ስድስት ሺህ ብር ወስደዋል›። የሰው ምስክሮችም ቀርበው ሟች እናት ቤት ሰርተው እንደነበረ ያረጋግጣሉ፡፡ ይህም ሆኖ የወ/ሮ አስካለ ማህደር ከቀበሌው ‹‹ጠፍቷል›› በመባሉ ምንም አይነት ማስረጃ ስላልቀረበ የቀድሞው ውሳኔ በይግባኝ ሰሚው ችሎትም ሊለወጥ አልቻለም፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮም ላለፉት ሁለት ዓመታት ከፍተኛው ፍርድ ቤት በር ላይ ቆሞ መጮኽን ስራዬ ብሎ ይዞታል፡፡ በርግጥ ከቀን ቀን አካላዊ መዳከም እየበረታበት መሄዱ በግልፅ ቢታይም የ40 ዓመቱ ጎልማሳ ሞገስ ወልዱ ዛሬም ከፍርድ ቤት ደጅ ቆሞ መጮኹና ማፏጨቱ የበርካታ ግፉአንን ድምፅ የሚወክል ይመስለኛል።

 

ይህ ጉዳይ የሚያሳየው፣ የመንግስት ደመወዝ እየተከፈላቸው በዜጎች ሕይወት ላይ ሊወስን የሚችል እንዲህ አይነቱን ማስረጃ ያለአንዳች ጭንቀት ‹‹ጠፋ›› ብሎ ለመናገር የሚደፍሩ፣ ስለሕዝብ ብሶትና ችግር ምንም ግድ የሌላቸው ካድሬዎች እየተበራከቱ መምጣታቸውን ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም እንደ ሞገስ ያሉ የፍትሕ እጦት ረመጥ ሆኖ ያንገበገባቸው ምስኪኖች በአደባባይ ሲጮኹ ውለው፤ ሲጮኹ ቢያድሩ ‹‹ምን ይሆን ችግራቸው?›› ብሎ ለማድመጥ የሚሞክር አንድ እንኳን ባለሥልጣን መታጣቱንም ጭምር ነው። ‹‹ሳይሰሙ ቀርተው ይሆናል!›› ማለቱን ከባድ የሚያደርገው ደግሞ፣ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አካባቢ የሚተላለፉ መንገደኞችም ሆኑ ወደ ተቋሙ የሚመጡ ባለጉዳዮች ክስተቱን የማወቃቸው እውነታ ነው፡፡ ከፖለቲካ ጋር በተያያዘ ፍርድ ቤት የሚቀርቡ ሰዎችን የችሎት ውሎ ለመሰለል ከተከሳሾች ቀድመው የሚደርሱ የደህንነት ሰራተኞችም ሞገስን ለማወቃቸው እኔው ራሴ ምስክር ነኝ። በአናቱም ከዚህ ቀደም በሸገር ራዲዮ ‹‹ኧረ በሕግ›› የሚል ፕሮግራም ያዘጋጅ የነበረውና በአሁኑ ወቅት በ97.1 ኤፍ.ኤም ‹‹የእኔ መንገድ›› የተሰኘ በተመሳሳይ ጭብጥ ዙሪያ የሚያተኩር ፕሮግራም የሚያዘጋጀው በሳሉ የሕግ ባለሙያ ሰለሞን ጓንጉል፣ ይህንን ታሪክ ከአንዴም ሁለቴ ለአድማጭ አድርሶታል፡፡ እንግዲህ እነዚህ ሁሉ ተደማምረው ነው ከቀበሌ አንስቶ ላይ ድረስ ያሉ መንግስታዊ መዋቅሮችን የዘረጋውና የሚቆጣጠረው የኢህአዴግ አመራር አባላት፣ የሞገስን ጩኸት ‹‹አልሰሙም›› ማለቱን ከባድ ያደረገው (በነገራችን ላይ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ግቢ ለአስር አመት ያህል በየቀኑ እየተመላለሱ የሚቆሙ አንዲት አዛውንት እና በፍትሕ ሚኒስቴር በር ላይ ቆማ መዋል ከጀመረች ስድስት ዓመት ያለፋት ራሄል የተባለች አቤት ባይ እንስት… መኖራቸውን አልዘነጋሁም)

 

ሙስና እና የጓዳ ፖለቲካ ትስስሮሽ

አገሪቷ በዚህ ሁሉ መፍትሔ እጦትና በፍትሕ መዛባት እየተመሰቃቀለችና በሕዝቦቿም ዋይታ እየተናወፀች ቢሆንም፤ መጽሐፉ ‹‹ዓይን አላቸው አያዩም፤ ጆሮ አላቸው አይሰሙም›› እንዲል፤ ገዥዎቻችን ይህን መሰሉን የድሆችና የአቅመ ደካሞች ብሶት መስማትን ፍፁም አይሹም። እነርሱ የታጋሉትም ሆነ የሚሰሙት አለቆቻቸውንና ባለፀጋዎችን ብቻ እንደሆነ ከሚያሳዩን በርካታ ማስረጃዎች መሃል ለአብነት አንድ ምሳሌ ላቅርብ፡-

 

ጉዳዩ በሙስና ተጠርጥሮ በእስር ላይ ከሚገኘው የቀድሞ ገቢዎችና ጉምሩክ ዳይሬክተር መላኩ ፈንቴ ጋር ይያያዛል፡፡ ከዚህ ሰው ሃያ አንድ ገፅ ከፈጀ የእምነት ክህደት ቃል ውስጥ ኮነ ምህረቱ የተባለ ግለሰብ በአራጣ ማበደር ተጠርጥሮ ከተያዘ በኋላ ‹‹እነአየለ ደበላ ለዳኛ ጉቦ ሰጥተው በዋስ ከእስር ተፈትተው፣ ከሀገር ለመውጣት ያስባሉ›› የሚል ‹‹መረጃ›› በመስጠት መተባበሩን ገብረዋህድ ወ/ጊዮርጊስ እንደነገረው ገልፆ፣ ከእስር እንዲለቀቅ መደረጉን እናገኛለን፡፡ መቼም በሙስና ወንጀል ከተጠያቂነት የሚድን ተከሳሽ የሚሰጠው መረጃ ተጠርጣሪዎችን በሕግ ለመጠየቅ የሚጠቅም ሲሆን እንጂ፤ እንዲህ ባለ ከዋናው ክስ ጋር በማይዛመድ ተራና የአሉ-ባልታ ወሬ አለመሆኑን እነገብረዋህድና እነመላኩ ቀርቶ ማንኛውም መንገደኛ እንኳ ሊጠፋው አይችልም፡፡ አውቆ የተኛ… እንደሚባለው ካልሆነ በቀር።

 

የሆነው ሆኖ ከመላኩ ፈንቴ የእምነት-ክህደት ቃል ትኩረት የሚስበው፣ ግለሰቡ በዚህ መልኩ ከሱ ተነስቶለት ከእስር ከተፈታ በኋላ ንብረቱና የባንክ ሒሳቡ መታገዱን አስመልክቶ የተፈጠረው ኩነት ነው፡፡ አቶ መላኩ ጉዳዩን ለመርማሪዎቹ ሲያብራራ ቃል-በቃል እንዲህ ነበር ያለው፡-

 

‹‹አቶ አባይ ፀሀዬ እና አቶ ደመቀ መኮንን ደውለው ‹ግለሰቡ አቤቱታ እያቀረበ ነው፡፡ ለምን አታዳምጡትም? ሲሉኝ፤ እኔም ከዚህ በኋላ ነው ግለሰቡን እቢሮዬ አግኝቼ ከላይ በገለፅኩት ሁኔታ እንዲስተናገድ ያደረኩት።››

 

እነዚህ ሰዎች ‹‹ነፃ አወጣነው›› የሚሉትን ሕዝብ ለስቃይ ዳርገው፣ ጥቂት ባለፀጎችን ብቻ ለማገልገል የቆሙ መሆናቸውን ለማስረገጥ ከዚሁ የእምነት-ክህደት ቃል አንድ ማሳያ ልጨምር፡- ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ የተባለ የአዲስ ልብ ህክምና ክሊኒክ ባለቤት ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው የሕክምና መሳሪያዎች (የልብ ፒስ ሜከር ተብሎ ተጠቅሷል) በሕገ-ወጥ መንገድ ሲያስገባ በቦሌ ኤርፖርት ጉምሩክ ሠራተኞች እጅ ከፍንጅ ከተያዘ በኋላ መለቀቁን በተመለከተ የህወሓት ከፍተኛ አመራር አባል የሆነው ዶ/ር ቴዎድሮስ አድህኖም ስልክ ደውሎ ‹‹ክሱን ብታነሱላቸውና በአስተዳደራዊ መፍትሔ ብትሰጧቸው›› ብሎ ከመንገሩም በላይ የግለሰቡ ክስ እንዲቋረጥ የሚጠይቅ ደብዳቤ እንደፃፈላቸው መላኩ ፈንቴ ለመርማሪዎቹ መናገሩ በመዝገቡ ላይ ተጽፎ ይገኛል፡፡ ይህንን ሁናቴም ከወቅቱ የፖለቲካ አሰላለፍ አኳያ ስንተነትነው አቶ መላኩ ‹ዶ/ር ቴዎድሮስን መስማት፤ ህወሓትን እንደመታዘዝ ነው› የሚል እምነት አድሮበት የተባለውን ፈፀመ ብለን ብንደመድም ተምኔታውያን አያሰኘንም፡፡

 

እነዚህ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ያውም ሀገር በሚጎዳ ወንጀል የተከሰሰ ተጠርጣሪን በተመለከተ ከሥልጣን ገደባቸው አልፈው ‹‹አድምጥ!›› እያሉ የማዘዛቸው ምስጢር ሥርዓቱ ለፍትሕ ያለውን ግድየለሽነት እና በዚህ ሥርዓት የሕግ የበላይነት ብሎ ነገር እንጦሮጦስ መውረዱን ፍንትው አድርጎ ያሳያል ብዬ አምናለሁ፡፡ በርግጥ ይህንን ጉዳይ ለጥጠን ከተመለከትነው ‹‹…ለምን አታዳምጡትም?›› የምትለዋን ቃል ሰምና ወርቅ የለበሰች ቅኔ አድርገን በመውሰድ ልንፈታት እንችላለን፤ በተለይም መላኩ ፈንቴ ከዚህች ጥያቄ መሰል ትዕዛዝ በኋላ ግለሰቡን ቢሮ ጠርቶ ማስተናገዱን ስናስተውል፡፡ ምንም እንኳን አባይ ፀሀዬ በጊዜው በጉዳዩ ላይ መላኩን ሊያዝበት የሚያስችል መንግስታዊ ሥልጣን /የዕዝ ተዋረድ/ ባይኖረውም፤ አንጋፋ የህወሓት አመራር አባልና የበለጠ የፖለቲካ ጉልበት ያለው መሆኑ፤ ደመቀ መኮንን ደግሞ በብአዴን በኩል የአለቃነቱ ነገር ሲታሰብ፣ አሁንም መላኩ ፈንቴ የተጠየቀውን ‹‹ጥያቄ›› ከማስተናገድ ውጪ ሌላ አማራጭ አይኖረውም ወደሚል ጠርዝ ይገፋናል፡፡ በርግጥ እውነታው ይህ ቢሆንም፣ መላኩ ዛሬም እስር ቤት ውስጥ ሆኖ የቀድሞ አለቆቹንም ሆነ ራሱን ተጠያቂ ለማድረግ አልደፈረም፡፡ በግልባጩ ለቀረቡበት ክሶች በሙሉ ተጠያቂው ገብረዋህድ እንደሆነ ከመናገሩም በላይ እንዲህ በማለት ወንጅሎታል፡-

 

‹‹የአያት ባለቤት በግብር ማጭበርበር ተከሶ በነበረበት ወቅት የተከሳሹ ቤተሰብ የሆነ ሰው እቢሮዬ መጥቶ ‹ገብረዋህድ ምንም ጥፋት ሳያጠፋ ነው የአያት አክሲዮን ማሕበር ባለቤትን ያሳሰረው፤ አሁንም አንድ ሚሊዮን ብር ካመጣችሁ ከእስር ይፈታል ብሎናል› የሚል ጥቆማ አመጣልኝ፡፡ …ገብረዋህድ እና ነጋ ገ/እግዚአብሔር (የነፃ ትሬዲንግ ባለቤት ነው) ጓደኛሞች ናቸው፡፡ ነጋ ዕቃ ሲያስመጣ አያስፈትሽም፤ የነጋም ጓደኞች እነ አልሳም፣ ጌት አስ የመሳሰሉት ድርጅቶች ዕቃ በቀላል ቀረጥና ታክስ እንዲሁም አልፎ አልፎ ሳይፈተሹ ያልፋሉ፤ …ባለቤቱ ሃይማኖትም፣ በነጋ ድርጅት ውስጥ ትሰራለች…››

 

መላኩ ፈንቴ ይህንን ጉዳይ ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ መናገሩንና ጠቅላይ ሚኒስትሩም፣ ፀጋዬ በርሄን ‹‹ተከታተል›› ብሎት እንደነበረ ከአስረዳ በኋላ እንደሚከተለው ይቀጥላል፡-

 

‹‹ገብረዋህድ በኋላ እንደነገረኝ ባለቤቱን ከነጋ ድርጅት አስወጥቶ በአዜብ ትዕዛዝ መሰረት ኤፈርት ውስጥ ያስቀጠራት መሆኑን ገልፆልኝ ‹አንተም ላይ የሚወራው ስለምትታገል ነው ብላኛለች አዜብ› ሲለኝ እኔም ተከታትዬ ፀጋዬ በርሄ ከምን እንዳደረሱት አልጠየኩም፡፡ መጠየቅ ነበረብኝ፤ ጥፋት ነው፡፡ በአጠቃላይ ገብረዋህድ ላይ ብዙ ነገር ይባል ነበር፡፡››

 

መቼም ይህ ምላሽ በ1981 ዓ.ም ከአስመራ ዩንቨርስቲ በኢኮኖሚክስ ዲግሪውን፣ ከአውስትራሊያ በገቢ አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪውን፤ ከለንደንም በቢዝነስ አስተዳደር በተመሳሳይ መልኩ ትምህርቱን ካጠናቀቀና የረዥም ዓመታት የስራና የፖለቲካ ተሞክሮ ካለው ሰው የተሰጠ መሆኑን ስናስተውል፤ ሀገሪቱ የአምባገነን ባለሥልጣናት መቀለጃ ብቻ ሳትሆን፤ የሰዎቹንም የአቅም ማነስ ያመላክታል፡፡ እንዲሁም እነሞገስ ሰሚ ያላገኙበትን ምክንያትም ሆነ በዚህች ሀገር ገንዘብ ያለው የፈቀደውን መፈፀም የመቻሉን ምስጢር ይገለፅልናል።

 

ኢህአዴጋዊ ዕድሜ ማራዘሚያ…

ገዥው ስብስብ የፍትሕ ስርዓቱን ተቋማዊነት ሳይነካ፣ ለጨቋኝነቱ መጠቀሚያ የሚያደርግበት አንዱ መንገድ ከጠቅላይ እስከ ታች በተዋረድ የሚገኙ ፍርድ ቤቶች ድረስ ያሉ ዳኞችን የሚመድብበት አካሄድ ነው፡፡ በርግጥ እንዲህ አይነቱ ሀገርና ሕዝብ አልያም ሞራላዊ ልዕልና እና የሕግ-የበላይነት የማያስጨንቀው አገዛዝ፣ የፍትሕ ስርዓቱ ቅጥ የለሽ ተባባሪነት ሳይታከልበት የሥልጣን ዕድሜውን ማራዘም እንደማይችል መረዳት አይሳነውም፡፡ ይህን ለማድረግም ያለው ብቸኛ ምርጫ ዳኞቹን ከስሩ መሰብሰብ ይሆናል፡፡ ለዚህ ደግሞ ኢህአዴግ መሩ-መንግስት ሁለት አካሄዶችን ለመተግበሩ ያሳለፋቸው ሁለት አስርታት በሚገባ ያሳያሉ።

 

የመጀመሪያው የሚሾሙት ዳኞች፣ የግንባሩ ከፍተኛ የካድሬ ማሰልጠኛ እንደሆነ ከሚነገርለት ሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ ተማሪዎች መካከል ማድረጉ ነው፡፡ ከዚህ ‹‹የትምህርት›› ተቋም ውስጥ የሚወጡ የሕግ ምሩቃን ደግሞ ስለጥልቅ ዘመናዊ የሕግ ፅንሰ-ሃሳብ ለማወቅ ከመትጋት ይልቅ፤ የኢህአዴግ ፖሊሲዎች እና አብዮታዊ ዲሞክራሲ ሕግን እንዴት ‹‹ለመደብ ጠላት›› መጠቀም እንደሚያስችሉ በሚሰብኩ መምህራን ስር እንዲያልፉ ይገደዳሉ (ስለመምህሮቹ ምሁራዊ ልሽቀት ለመረዳት የሕዝብ ሙስሊሙን ጥያቄ በሽብር ተግባር ለመፈረጅ እና ማሕበረ ቅዱሳንን በአክራሪነት ለመወንጀል በ‹‹ጥናታዊ ጽሑፍ›› ስም የተጓዙበትን ርቀት ማየቱ ብቻ በቂ ይመስለኛል)፡፡ ተማሪዎቹም በዚህን መሰሉ የካድሬ ተቋም ስልጠና ስር ሰንብተው ሲወጡ፤ በፍፅምና ሊታመኑላቸው ይገቡ የነበሩትን ፍትሓዊ ዳኝነትና ህሊና የሚባሉ ጉዳዮችን ጨፍልቀው፣ በተለይም ፖለቲካዊ ነክ በሆኑ አይረቤ ክሶች ፊታቸው በሚቆሙ ንፁሀን ዜጎች ላይ መከራን የሚያዘንቡ አሽከሮች ይሆናሉ፡፡ ይህንን አስነዋሪነት ካለመታከት የሚፈፅሙትም፣ ሥልጣንን እና ተያያዥ ጥቅማ-ጥቅሞችን እያጋበሱ ወደ ከፍታ ሲወጡ ተመልክተናል።

 

ሁለተኛው የግንባሩ አካሄድ ከካድሬ ማሰልጠኛውም ሆነ የተሻለ ነው ከሚባለው የአ.አ.ዩ. የሕግ ፋካሊቲ የሚመረቁትን፣ በተከታታይ ርዕዮተ-ዓለማዊ ጠመቃ የሥርዓቱ ጋሻ-ጃግሬ ማድረግ ላይ ያተኮረው ነው፡፡ በሀገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች ሲያገለግሉ ቆይተው ስደትን የመረጡ ዳኞችና ዐቃቢ-ህግያት በተለያየ ጊዜ እንደ መሰከሩትም አሰልቺ የርዕዮተ-ዓለም ጠመቃ የፍትሕ ሥርዓቱን ነፃነት ጽልመት ካላበሱት ሂደቶች በዋነኛነት ተጠቃሽ ነው፡፡ በአንድ ወቅትም ሟቹ አቶ መለስ ዜናዊ የሀገሪቱን ዳኞች ሰብስቦ ስለሕገ-መንግስት እና ሕገ አተረጓጎም መርህ ሲያስተምር ለማየት የተገደድነው የዚሁ የጠመቃው አንድ አካል በመሆኑ ይመስለኛል፡፡ ዳሩስ፣ ይህማ ባይሆን ኖሮ እስክንድር ነጋ ላይ 18 ዓመት መፍረድ ሕሊና እንዴት ይፈቅድ ነበር? ኦልባና ሌሊሳንስ ለ11 ዓመታት ወህኒ ያስወረወረው ጥፋት ምን ተብሎ በአሳማኝ መልኩ ሊጠቀስ ይችል ይሆን?

…ቀሪው ለሳምንት ይቆየን!

የምእራብ ጎጃም ነዋሪዎች በመብራት እጦት መማረራቸውን ገለጹ

$
0
0

ethsatመጋቢት ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን በፍኖተ ሰላም እና አጎራባች ወረዳዎች ማለትም በቡሬ ፤ በጃቢ ጠናን ፤ ፈረስ ቤት ፤ ይልማና ዴንሳ፣ ፤ሜጫ ፣ አቸፈር እና ቋሪት የሚኖሩ ነዋሪዎች በፍኖተ ሰላም ከተማ በጃቢ አዳራሽ ከመልካም አስተዳደር ችግሮች ጋር በተያያዘ ከክልሉ መስተዳደር ጋር በተደረገ ውይይት በመብራት እጦት ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን በምሬት ተናግረዋል።

የመብራት ሃይል ሹሞች በሙስና ተዘፍቀዋል ያሉ አንድ ተናጋሪ ፤ ስራቸውን ለመስራት ጉቦ እንደሚጠይቁዋቸውና ለሚመለከታቸው የመንግስት ባለስልጣናት አቤት ሲሉም የሚሰማቸው ማጣታቸውን ገልጸዋል።

የፖሊስ ባልደረባ የሆኑት ዋና ሳጅን አለማየሁ አዲስ በበኩላቸው መብራት ሃይል መንግስት የማያውቀው በራሱ የሚመራ ድርጅት መሆኑን አስታውሰው፣ ቅሬታችንን ለመንግስት አካላት ስናቀርብ ፖሊሱ ፣ ነዋሪው እንዲሁም ሚኒስትሩ ሳይቀር አሸባሪ ተብሎ እየተፈረጀ ነው ብለዋል።

ዘመኑ አሰፋ የተባሉ የፉነተሰላም ነዋሪ በበኩላቸው በውስጥ ለውስጥ መብራት ችግር ምክንያት የማታ ተማሪዎች በተለይ ሴት ተማሪዎች ለአደጋ እየተጋለጡ መሆኑን ገልጸዋል

Source: Ethsat

ሰበር ዜና፡- ወ/ሮ አስቴር ማሞ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ ተሾሙ

$
0
0

ሪፖርተር  ጋዜጣ

ወ/ሮ አስቴር ማሞ

ወ/ሮ አስቴር ማሞ

በቅርብ የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ በኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት በተመረጡት አቶ ሙክታር ከድር ምትክ፣ ወ/ሮ አስቴር ማሞ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደርና ሪፎርም ክላስተር አስተባባሪ ሆነው ተሾሙ፡፡

ማክሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. በፓርላማ ሹመቱ የፀደቀላቸው ወ/ሮ አስቴር በተጨማሪ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አቅራቢነት በፓርላማው ሹመታቸው የፀደቀው ወ/ሮ አስቴር የመጀመርያዋ ከፍተኛ ተሿሚ ናቸው፡፡

‹‹ሴት ተሿሚ ለዚህ ከፍተኛ ሹመት በማቅረቤ ከፍተኛ ደስታ ይሰማኛል፤›› ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለፓርላማው አባላት ስሜታቸውን ገልጸዋል፡፡ ወ/ሮ አስቴር ሹመታቸው ከፀደቀ በኋላ ቃለ መሐላ ፈጽመዋል፡፡

በተለያዩ ከፍተኛ የፓርቲና የመንግሥት ኃላፊነቶች ላይ የቆዩት ወ/ሮ አስቴር፣ በፓርላማው የመንግሥት ተጠሪ የነበሩ ሲሆን እስከ ሹመታቸው ድረስ በምክትል ፕሬዝዳነት ማዕረግ የ ኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አማካሪ ነበሩ፡፡

“አኬልዳማ” ኢቴቪን ካሣ ሊያስጠይቅ ነው

$
0
0

ኢቴቪ የማረሚያ ፕሮግራም እንዲያስተላልፍ ፍ/ቤት አዟል
“መልካም ስሜን የሚጠግን ተመጣጣኝ ፕሮግራም ሠርቼ አቀርባለሁ”

hqdefaultየኢትዮጵያ ቴሌቪዥን  ባስተላለፈው “አኬልዳማ” የተሰኘ ዘጋቢ ፊልም፣ መልካም ስሜን አጉድፏል ሲል አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ፤ኢቴቪን መክሰሱ የሚታወስ ሲሆን ሰሞኑን የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት በሰጠው ውሣኔ፣ ጣቢያው ቀደም ብሎ ለ“አኬልዳማ” በሰጠው የአየር ሽፋን መጠን የሚቀርብ፣ በፓርቲው ላይ የደረሰውን ጉዳት የሚያካክስ ፕሮግራም ሠርተው ያቅርቡ ሲል ትእዛዝ አስተላልፏል፡፡
አንድነት በበኩሉ፤ በፍ/ቤቱ ትዕዛዝ መሠረት መልካም ስሜን የሚጠግን፣ተመጣጣኝ ፕሮግራም ሠርቼ አቀርባለሁ፤ ለደረሰብኝ የወጪ ኪሣራም ተገቢውን ካሣ እጠይቃለሁ ብሏል፡፡
ፍ/ቤቱ በሰሞኑ ውሣኔው ተከሳሽ (ኢቲቪ)፤ ከህዳር 16 እስከ ህዳር 18 ቀን 2004 ዓ.ም በጣቢያው ባስተላለፈው “አኬልዳማ” ዘጋቢ ፊልም፣ ከሣሽን  ከግንቦት 7 የሽብር መረብ አንዱ መሆኑን፣ አባላቱም ብጥብጥና ሁከት ፈጣሪ መሆናቸውን፣ ለአሸባሪዎች አመራርና አባላቱ ሽፋን እንደሚሰጡ በማመላከት ዘገባ ማቅረቡንና የፓርቲውን ስም ማጥፋቱን ጠቅሶ  ድርጊቱ አግባብ አይደለም ብሏል፡፡ በዚህም መሰረት ተከሣሽ ይሄንኑ ዘገባ በሚያርም መልክ ተመጣጣኝ ፕሮግራም በጣቢያው እንዲያስተላልፍ ወስኗል፡፡ ከሣሽ በዚህ ክስ ምክንያት የደረሰበትን ወጪ ዘርዝሮ፣ ተከሣሽን ካሣ የመጠየቅ መብቱ የተጠበቀ እንደሆነም ፍ/ቤቱ ገልጿል፡፡
“ፍ/ቤቱ ለደረሰብን የሞራልና የቁስ ኪሣራ ካሣ መጠየቅ እንደምንችል በውሳኔው ስላመለከተ፤በዚህ መሠረት ተገቢውን ካሣ አስልተን እንጠይቃለን” ብለዋል- አቶ ሃብታሙ፡፡
በፍ/ቤቱ ውሣኔ ሙሉ ለሙሉ አለመርካታቸውን የገለፁት ሃላፊው፤“በተለይ በሽብር የተከሰሱት ግለሰቦች ጉዳያቸው በፍ/ቤት የተያዘ መሆኑ እየታወቀ፣ ከህግ አግባብ ውጭ በንፁህ የመገመት መብታቸውን ተነፍገዋል” ለሚለው የፓርቲው የክስ ነጥብ፣ ውሣኔ አለመሠጠቱ ቅር እንዳሰኛቸው ጠቁመው፤አሸባሪ የተባሉት ግለሰቦች ነፃ እስኪወጡ ድረስ የፓርቲው ትግል እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡
በሌላ በኩል አንድነት ፓርቲ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከሚያካሂደው ሠላማዊ ሠልፍ ጋር በተገናኘ ከአስተዳደሩ ጋር አለመግባባት መፈጠሩንና ፓርቲው ያቀረባቸው ሶስት  አማራጭ  ቦታዎች ውድቅ መደረጋቸውን አቶ ሃብታሙ ጠቅሰው፣ አስተዳደሩ ሠልፉን ለማደናቀፍ  እየሞከረ ቢሆንም ፓርቲያቸው ሠላማዊ ሠልፉን ከማከናወን ወደ ኋላ እንደማይል ገልፀዋል፡፡

 


ኢትና አሸሮች፥ የህወሃት የድሜ ልክ እስረኞች (ሳዲቅ አህመድ)

$
0
0

ገና ወጣት ሳሉ የደርግን ስርዓት በመሸሽ ወደ ጠረፍ ያቀኑ ናቸዉ። ዲሞክራሲያዊ መሆን ይቃጣዉ የነበረዉ ህወሃት ሁለት አማራጭ የሰጣቸዉም ነበሩ፤ ደርግን በጦር መታገል ወይም ሱዳን ገብቶ ስደተኛ በመሆን ወደ አዉሮፓ፣ዩናይትድ እስቴትስ ወይም ካናዳ በመሰደድ ህወሃትን በገንዘብና በፖለቲካ መርዳት። ወደ ጦርነት አዉድማ የገቡት ኢትና አሸሮች  እንዳሉ ሆነዉ ሱዳን መግባት የመረጡት በተባበሩት መንግስታት (UNHCR) በኩል ወደ ምእራቡ አለም የመጓዛቸዉ ህልም እዉን እስኪሆን ድረስ በሱዳን ዉስጥ “ኢትና-አሸር” የሚባል ህገወጥ (ሐራም) ስራ ነበራቸዉ። ለአያሌ አመታት በዚህ ህገወጥ ስራ በመሰማራት ህወሃትን የደገፉ ሲኖሩ እነዚሁ ኢትና አሸሮች ዛሬም ካሉበት ቦታ የህወሃት የቁም እስረኞች ሆነዉ ህወሃትን እያገለገሉ ይገኛሉ።

ኢትና አሽር (አስራ ሁለት)የስራ ዘርፍ ምን እንደሆነ ለኔ ለመጻፍ በጣም ያሳፍረኛልና ሱዳን ከነበሩ ኢትዮጵያዉያን ጠይቃቹ ተረዱ። ሰዎችን በሙስና ይዞ ሎሌ ሚያረገው ህወሃት፤ እነዚህንም ኢትና አሽሮች ባሰራቸዉ አሳፋሪ ወንጀል ዛሬም ከርቀት ሆኖ ይቆጣጠራቸዋል።አንዳንዶቹ ንሰሃ አርገዉ ቤተ-ክርስቲያን ወይም ተዉበት አርገዉ መስጊድ ቢገቡም፤ የካድሬነት ስራ ይሰጣቸዋል። ስለ ቤተ ክርስቲያኑ ባላዉቅም ስለ መስጊዱ ትንሽ ልበል…

ኢትና አሸሮች ምን ያደርጋሉ?

ስርዓቱን ሊነካ የሚችል ስራ ለመስራት ስብሰባ ቢጠራ ስብሰባዉን ንግግር በማስረዘም ማበላሸት፣ከተሰብሳቢዉ ጋር ችግር በመፍጠር ስብሰባዉን የጭቅጭቅ ማድረግ፣ሰላማዊ ሰልፍ ሲጠራ ቢቻል ሰላማዊ ሰልፉን ማስቀረት ካልሆነ ሰላማዊ ሰልፉ ደካማ እንዲሆን ማድረግ፣ሚስጥርን ለህወሃት አሳልፎ መስጠት፣ “እኔ ከዚህ ዘር ስለሆንኩኝ ነዉ የማልታመነዉ” በማለት ማለቃቀስ፣ በህዝብ ዘንድ የማይደገፍ ሐሳብ ሲሰነዘር ደካማዉን ሐሳብ በመደገፍ ተክቢርን ማዥጎድ ጎድ፣ ፊትና (መከፋፈል) መጣ ብሎ በማልቀስ የሰዉን ልብ በልቶ አቅጣጫ ማስቀየር፣ስርዓቱን በጽኑ የሚቃወሙ ግለሰቦችንና ሚዲያዎችን ስም ማጥፋትና ተዓማኒነትን ማሳጣት ወዘተ የገኙበታል።

ኢትና አሸሮች ዲያስፖራ ባሉ ቡድኖች በቦርድ-በሃላፊነት ተመርጦ ለመስራት የማያቅማሙ ሲሆኑ በተለያዩ ኮሚኒቲዎች በሃላፊነትም ይሰራሉ፤ አንዳንድ የኑሮን እንቅፋቶች ህወሃት ሰለሚያነሳላቸዉ ከሌላዉ የበለጠ ግዜን መለገስ ብቻ ሳይሆን ዳጎስ ያለ ገንዘብን አዉጥቶ በመርዳት የሰዉን አፍ ለማዘጋት ይሞክራሉ። ሰዎችን በጥቅም ለመደለል የሚያረጉት ሙከራ የላቀ ነዉ፤ በመንግስትና በዲያስፖራዉም መሃከል ድልድይ በመሆን ባመራር ደረጃ ላይ ላሉ ወገኖች በኢንቨስትመንት ስም መሬት በማሰጠትና ሌሎችንም ለሙስና የሚመቹ ጉዳዮችንም ያስፈጽማሉ።

ምክር፥ ዉድ ኢትና አሸሮች! ዉድ የሆነዉን ህይወት ለህወሃት አሳልፎ ሰጥቶ የቁም እስረኛ ከመሆን የትላንቱ ታሪካቹ የትላንት ነዉና ዛሬ የናንተን የበደል ገፈት የቀመሱ እህቶችን ይቅርታ ጠይቃቹ፤ አምላክቹን ጥልቅ በሆነ ንሰሃ (ተዉባ) ተማጸኑትና እራሳ ሁን ከህወሃት ቀንበር ነጻ አዉጡ።

ምክር፥በኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች የእምነት ማእከላትና ማህበራት ዉስጥ ተሸጉጣቹ የሙስሊምን ሰላማዊ ትግል እንቀለብሳለን ብላቹ የምታምኑ ከሆነ ከንቱዎች ናቹ። የሰሞኑም ግርግራቹ አልሰራም(ያዲሳባዉም ጭምር)፤ እናንተ ለሰራቹት የኢትና አሸር ሐጢዓት ይቅርታ ጠይቁ እንጂ ድምጻችን ይሰማ” የሚለዉ ጀግና ትዉልድም ሆነ መሪዎቹ ከማፍያዉ ህወሃት የላቁ በመሆናቸዉ ይቅርታ አይጠይቁም። ግዜዉ ሳይረፍድ የህወሃትን ሲህር (መተት) ከላያቹ ላይ ገፋቹ ጣሉና ከጀግናዉ ትዉልድ ጋር አብራቹ ጀግኑ።

ዉዱ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! እነዚህ ኢትና አሸር የምንላቸዉ ንዑሳንን ሴራ ለማሳየት በጃችን ያለዉን የድምጽና የቪዲዮ መረጃ ብንለቀዉ “ለካስ አልቀናል” ብሎ ብዙሓኑ ይደናገጣል። ተወደደም ተጠላም  ለህዝብ በነጻ (ሊላሂ) እንሰራለን የሚሉ የዲያስፖራ ቅምጥሎች ይህን ሰላምዊ ትግል ለማዳከም እንዳልዳከሩት የለም…ግን ዉድቀት ታትማባቸዉለች አሸናፊ አይሆኑምና ልብ ያለዉ ልብ ይበል!

ሳዲቅ አህመድ

 CLK

 

 

ብርሃኑ ዳምጤ –ደቡር አባ መላ ዘአገምጃ

$
0
0

 መስፍን ቀጮ/ወፍ
ከጠቅላይ ቢሮ አዲስ አበባ

Aba-Mela  የሚቀጥለውን ትረካ ለመጻፍ ብዙ ሀሳብ ውስጥ ገብቼ ነበር፡፡ ብጽፈውስ ምን ዋጋ አለው የሚል ስሜትም ተጭኖኝ ነበር፡፡ ሆኖም ‹ጅብ በማያውቁት ሀገር ቁርበት አንጥፋልኝ› እንዲሉ ከላይ የተጠቀሰው ብርሃኑ ደቡር አባ መላ በአዲሶቹ አለቆቹ የተረቀቁለትን ቃለ መጠይቆች ሲያነበንብ መስማቱ ስለሰለቸኝ ‹ማን ያውጋ የነበረ ማን ያርዳ የቀበረ› በማለት የልጅነት ጓደኛዬን ሳልወድ ለማጋለጥ ወሰንኩ፡፡

እኔና ብርሃኑ ዳምጤ በአንድ ማዕድ እየበላን በሰፈር ወንዝ እየተራጨን እየተንቦራጨቅን ብይና አርቦሽ እየተጫወትን ሌላም ሌላም ነገር እየሰራን ያደግን ልጆች ነበርን፡፡ ብርሃኑና እኔ ት/ቤት ስንገናኝ እንዲሁ ጓደኛሞች ሆነን እኔ ከእሱ በዕድሜ አራት ዓመት አንስ ስለነበር ትምህርት የጀመርኩት ከሱ በኋላ ነበር፡፡ አንደኛ ክፍል ስገባ እሱ ወደሶስተኛ ተዛውሯል፡፡ ከሱ በእድሜ ከማነሴ በላይ ደቃቃ በመሆኔ ‹ቀጮ› የሚል ቅፅል ስም ወጥቶልኝ ነበር፡፡ ብርሃኑ በዚያን ጊዜ ከክፍል ልጆች በዕድሜ ይበልጥ ነበር፡፡ በትምህርቱ ደካማ ስለነበር ክፍል ስለሚደግም ታናናሾቹ ይደርሱበትም ይቀድሙትም ነበር፡፡ ለዚህም ነው እኔና እሱ ስድስተኛ ክፍል ላይ የተገናኘነው ብርሃኑ በጣም ወፍራምና ለፍላፊ ነበር፡፡

ሲለፈልፍ በፍንጭቱ ይረጨው የነበረው ምራቅ ከውፍረቱ ጋር ሆኖ ትርክርክነቱን ያጎላው ነበር፡፡ አንድ የጠቅላይ ግዛት ልጅ ‹የድሃ መሃቻ› (ሊጥ ማቡኪያ) ብሎ ጠራው፡፡ ከዚያ በኋላ የድብቅ መጠሪያ ስሙ ሆነ፡፡ ብርሃኑ ምግብ በተለይ ጥሬ ሥጋና እንቅልፍ ከሁሉም በላይ አብልጦ የሚወድ ልጅ ነበር፡፡

ከስድስተኛ ክፍል በኋላ እኔና ብርሃኑ በጣም ጥብቅ ጓደኛሞች ሆንን ብርሃኑን የተጠጋሁት የሰፈር ጉልቤዎች በሚተናኮሉኝ ጊዜ ይከላከልልኝ ስለነበር እሱ የወደደኝ ደግሞ ክፍል ውስጥ የቤት ስራም ሆነ ፈተና ስለማስገለብጠው ከዚያም አልፎ ከትምህርት ቤት በኋላ እቤቴ ሸኝቶኝ ምግብ በልቶ ስለሚሄድ ነበር፡፡ በወላጆቼ በኩል ከቀልደኝነቱ ባሻገር አንድ ልጃቸው በመሆኔ እንደ አይነ ብሌናቸው ያዩኝ ስለነበር ወንድም በማግኘቴ ደስ ብሏቸው ይወዱት ነበር፡፡

የስድስተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ተፈትነን ውጤት ሳንሰማ በክረምት ወር አባቴ በመስሪያ ቤቱ ትዕዛዝ ወደ ጠቅላይ ግዛት በመዛወሩ እኔም አብሬ ተጓዝኩ፡፡ በሶስተኛ ዓመት ክረምት ላይ ለዕረፍት አዲስ አበባ መጥቼ ስለነበር ጓደኛዬን ለማግኘት ሰፈር ስሄድ አያቶቹን ሊጠይቅ አገምጃ ጉራጌና ኦሮሞ አገር መሄዱ ተነገረኝ፡፡ በነገራችን ላይ ብርሃኑ በአባቱ መንዜ ሲሆን በእናቱ ደግሞ የአገምጃ ጉራጌና ኦሮሞ ነው፡፡ ሳላገኘው በመመለሴ እያዘንኩ ወደ ጠቅላይ ግዛት ተመለስኩ፡፡ በዓመቱ አባቴ እንደገና ወደ አዲስ አበባ በመዛወሩ ተመልሼ አዲስ አበባ መጣሁ ብርሃኑንም ወዲያው አገኘሁት፡፡

ብዙ ገጠመኞቻችንን እየተለዋወጥን እንደቀድሟችን አብረን መጫወትና መዋል ቀጠልን፡፡ ታዲያ መስከረም ጠባና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታችንን ስንጀምር እኔ ከአስረኛ ክፍል ልጆች ጋር ስሰለፍ ጓደኛዬ ከዘጠነኞች ጋር ተሰልፎ አየሁት፡፡ ሚኒስትሪ በመውደቁ አንድ ዓመት ደግሟል፡፡ አልገረመኝም ጓደኛዬን ስለማውቀው!

ከስልሳዎቹ መጀመሪያ የኃይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሚያንቀሳቅሱት የመንግስት ተቃውሞና አመጽ እየበረታ  በሄደበት ወቅት የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችን ቀልብ ስቦ የእንቅስቃሴው አጋርና ደጀን አድርጓቸው እንደነበር ይታወሳል፡፡ ስድስትና አራት ኪሎ በተነቃነቁ ቁጥር መላው የአዲስ አበባ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ይንቀሳቀሳሉ፡፡ ወረቀት ይበተናል፣ የከተማ አውቶቢስ ይሰባበራል፡፡ ሌላም ብዙ ሌላ ነገር ይደረጋል፡፡ በዚያን ወቅት የመርካቶን ተማሪዎች የምናስተባብረው ብርሃኑ፣ እኔ፣ ተስፋዬ የማነና ሌሎም ነበርን፡፡ ተስፋዬ የማነ ችኩል ቅብጥብጥ ግብታዊና ደፋር ነበር፡፡ ይህን ስለምናውቅ አደገኛ ሁኔታዎችን እንዲፈጽም እናደርገው ነበር፡፡ አንድ የማልረሳውና እስከ አሁን ድረስ የሚፀጽተኝ ነገር ላውራችሁ፡፡ ከሰፈር ወጥተን ልክ ጠቅላይ ቢሮ ስንደርስ ሹፌሩ ብቻ ያለበት አንድ አውቶቢስ ቆሞ እናያለን፡፡ አውቶቢሱ ብቻ ለምን እንሰብራለን ሹፌሩም መመታት አለበት አለ ብርሃኑ ችኩልና ቅብጥብጡ ተስፋዬ ዕብድ በሚያክል ድንጋይ የሾፌሩን አናት ተረከከው፡፡ ምስኪኑ ሹፌር

የተማሪዎች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ የየካቲትን አመጽ አስከተለ፡፡ አመጹ በመካሄዱ ላይ እንዳለ ከውጪ የመጡ ምሁራንና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በየፊናቸው ሕቡዕ ጥናት ክበቦችን በማቋቋም ወጣቱን መመልመል ተያያዙት፡፡ በዚህም መሰረት ኢህአፓና መኢሶን ወጣቱን እየተቀራመቱ በየጎራቸው ኮለኮሉት ታዲያ ብርሃኑ፤ ተስፋዬና እኔ የኢህአፓ ሰለባዎች ሆንን፡፡ እንደማንኛውም ወጣት የድርጅቱ ተገዢና ደጀን ለመሆን በሙሉ ልብ ተሰናዳን፡፡ ከብዙ ፈተናና ምስጢራዊ ግምገማ በኋላ ታማኝነታችን በመረጋገጡ ከበላይ አካል የሚሰጠንን ሚሽኑ (ግዳጅ መፈጸም ጀመርን) በዚህ ወቅት ነበር፡፡ ብርሃኑ ዳምጤ ‹‹ደቡር›› የተሰኘውን የኮድ ስም የተጎናጸፈው እኔም ከቀጮ ወደ ‹‹ወፍ›› ተቀየርኩ፡፡ የተስፋዬን ረሳሁት፡፡ በድርጅቱ መዋቅር መሠረት እኔ በቅርብ እንዳውቃቸው የተደረጉት ተስፋዬና ብርሃኑ ደቡር ብቻ ነበሩ፡፡ በደቡር በኩል እየተነገረኝ ከበላይ የሚፈሰውን መመሪያና ግዳጅ መፈጸም የቀን ተቀን ተግባራችን ሆነ፡፡

ከትዝታዎቹ አንድ ቀን ደቡር ግዳጃችንን ነገረን ይኸውም ምዕራብ ሆቴል ጀርባ አንድ ሀብታም ነጋዴ የቀን ገቢውን ማታ ማታ ቤቱ ይዞ ስለሚሄድ መኪናው አካባቢ በመቆየት ገንዘቡን ተረክቦ መሄድ ስለሚሆን ሁለት የታጠቁ ጓዶች በአካባቢው እንደሚገኙና ወፍ የተቀዳደደ ልብስ ለብሰህ ማዘናጋት ትጀምራለህ ተባልኩ፡፡ ወዲያውም ጓዶቹ አስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳሉ፡፡ ሰውየውን ገና ስጠጋው ጓዶቹ ከመቅጽበት መጥተው ገንዘብ ተረክበው ይባስ ብለው የሰውየውን ፔጆ መኪና ቁልፍ ነጥቀው አስነስተው ፈረጠጡ ወደ መደበቂያችን ቦታ ሄድኩ፡፡ ደቡርና ተስፋዬ ቤቱን አሟሙቀው ጫት እየቃሙ ደረስኩ፡፡ በምርቃና የተለያዩ እቅዶችን ስናወጣና ስናወርድ ቆይተን ወደ ጨብሲ ተዘዋወርን፡፡ ብዙ ስንገነባና ስናፈርስ አድረን፡፡ የበላይ አካልን ትዕዛዝ እንጠብቃለን፡፡ ራሳችን በግብታዊነት፣ በጠላት ስም ሰዎችን እረሽነናል፡፡ ሚሽን ከሌለን ሥጋ መጠጥና ጫት አስገዝተን ለሌላ ግድያ እንዘጋጃለን፡፡ ቀልቤሳ በቀበሌ የኛ ግፍና ጭካኔ ደግሞ ከሱ ቢበልጥ እንጂ አያንስም፤ ምን ዋጋ አለው ለአንባቢያን ማቅረቡ እኔን ራሴን ስለሚዘገንነኝ ዝም ብዮ እዘጋዋለሁ፡፡ ባለፈረሱ ብርሃኑ ደቡርስ ምን ይሰማው ይሆን? እንደ አርበኞችና ጀግኖች እሱም ባለፈረስ ሆነ አባነብሱ፣ አባዳኜ፣ አባጠቅል፣ ሲባል ሰምቶ ብኩን አረመኔ!

ትግሉ እየጋለ በሄደ ቁጥር የመኢሶንና የኢህአፓ ጦርነት እየተፋፋመ ሄደ፡፡ በዚህም ጊዜ ራስን ለማዳን ወይም ለአላማ ብዙ ጓዶች ተገድለዋል፡፡ እኛም ብዙ ረፍርፈናል፡፡ ብዙ ሀብታሞችን አስገብረናል፡፡ የንጹህ ሰዎችንም ደም በከንቱ አፍሰናል፡፡ ቤት ይቁጠረው፡፡ ከአሜሪካን ግቢ ጀምሮ አደሬ ሰፈርን ሰባተኛን ኮልፌን አካሎ በአሸባሪነትና በገዳይነት የታወቀው ስም ደቡር የዛሬው አባመላ ከነህዋሱ ነበር፡፡ ሁኔታዎች እየከፉ ሄደው በቀበሌና በደርግ ፖሊሶች ኢህአፓ፣ መመታት ጀመረ፡፡ ይባስ ብሎም ኢህአፓ ለሁለት ተከፈለ፡፡ በመሆኑም የኢህአፓ መዋቅር ውዝምብር ውስጥ በመግባቱ ግማሹ ወደ አሲንባ፣ ሸዋና ወሎ ገጠር ውስጥ ሲገባ ግማሹ ደግሞ ከተሞች ውስጥ መፍጨርጨር ጀመረ፡፡ እኔ አዲስ አበባ ስቀር ደቡርና ተስፋዬ ወደ አጋምጃ ሸፈቱ፡፡ ሩቅ ሳይሄዱ አንዲት ትንሽ ሆቴል አልቤርጎ ውስጥ ተማርከው ወደ አዲስ አበባ ተወሰዱ፡፡ ወሬውን ስሰማ በጣም አዘንኩ፣ ተደናገጥኩ፡፡ ተደብቆ መኖርንም ተያያዝኩት፡፡ ከጥቂት ወራቶች በኋላ ተስፋዬን አገኘሁት፡፡ እንደኔው ተጨናንቆና ተደናግጦ ነበር፡፡ ከእስር እንዴት እንደተፈታ አላጫወተኝም፡፡ የመጨረሻ መተያየት ሆነ፡፡ ሰንብቼ ስጠይቅ ተስፋዬ የማነን እህቶቹ ወደ አሜሪካ እንደወሰዱት ሰማሁ፡፡ አይ ቅብጥብጡ ተስፋዬ አሁንስ ሰክኖ ይሆን?

ከኢህአፓ መሰነጣጠቅ በኋላ ብዙ ጓዶች ለደርግ እጃቸውን ሰጡ ይቅርታ እየጠየቁ፡፡ አንድ ምሽት በተደበቁበት ቦታ ከብርሃኑ ደቡር የኮድ መልዕክት ደረሰኝ፡፡ በጣም በመገረም ወደ ቀጠሮው ቦታ ሄድኩ፡፡ በኮድ መሠረት ወደተባለችው ላንድክሩዘር ተጠጋሁ፡፡ ደቡር ጋር አይን ለአይን ተያየን፡፡ መኪናው ውስጥ ገባህ ተሳሳምን፡፡ መኪናዋ መንቀሳቀስ ጀመረች፡፡ ከጥቂት ቆይታ በኋላ መኪናውን ከሚሾፍረው ሰው ጋር አስተዋወቀኝ፡፡ ቀጥሎም መጠነኛ የፖለቲካ ትንታኔ ካደረገልኝ በኋላ ግራ የሚያጋባ ሚሽን (ግዳጅ) እንዳለን ገለጸልኝ፡፡ ይኸውም ጓዳችን የሆነው ጩልሌ (መላኩ) መመታት እንዳለበት በበላይ አካል መወሰኑን ነገረኝ፡፡ ጥርጣሬ ላይ ወደቅሁ፡፡ በማን? በደርግ? ወይስ ከሁለቱ የኢህአፓ አንጃዎች ባንዱ? ግራ ገባኝ፡፡ ብርሃኑ ደቡርና ሰውየው ጉንጫቸው በጫት ተወጥሮ ነበር፡፡ ጨብሲ እናድርግ ብለው ሰንጋ ተራ አካባቢ መኪናዋን አቆሙ፤ አንዲት ትንሽ መጠጥ ቤት ገብተን ቢራዎች መጠጣት ጀመርን፡፡ ከሁለት ሰዓት ቆይታ በኋላ ከቤቷ ወጥተን ወደ ተክለሃይማኖት አቀናን ጎላ ሰፈርን እንዳለፍን የተዋወቅኩት ሾፌር መኪናዋን አቁሞ ወረደ፤ ከመንገዱ ዳር ካለች የተዘጋች ኪዩስክ ጠጋ ብሎ ከአንድ ህፃን ጋር ተነጋግሮ ወደ መኪናው ተመለሰ፡፡ ወዲያውኑ ደቡር ክላሽንኮቭን ከመኪናው ወለል አንስቶ የመኪናውን የጎን መስታዋት አወረደ፡፡ ከትንሽ ደቂቃዎች በኋላ ጩልሌ (መላኩ) ከመንገዱ ዳር ሲደርስ ብርሃኑ ደቡር የያዘውን ክላሽ አቅንቶ ጥይቱን አርከፈከፈበት፡፡ በሰኮንዶች ጊዜ ብትንትኑ ወጥቶ መሬት ላይ ተዘረረ፡፡ መኪናዋም በሀይለኛ ፍጥነት እየበረረች ሰፈሩን ለቀቅን፡፡ ብዙ ግድያዎች ላይ ተሳትፌአለሁ፡፡ እንደዛች ቀን ግን ደንግጨና ፈርቼ አላውቅም፡፡ እስከዛሬ ህሊናዬን የሚያስጨንቀኝ ነገር ቢኖር ጩልሌን ለምን? ነበር፡፡

ደቡርስ አሁን ምን መልስ ይሰጠን ይሆን ወይስ እንደጲላጦስ እጁን ታጥቧል፡፡ ጉዞዋችንን በመቀጠል ፒያሳን ካቋረጥን በኋላ በራስ መኮንን ድልድይ አካባቢ እንደገና አንድ ቡና ቤት ውስጥ ገባን፡፡ እኔ እየተርበተበትኩ ነው፡፡ እነሱ ግን በጫቱና በጨብሲው ምክንያት የደፈረሱትንና ቦታ የጠበባቸውን አይኖቻቸውን እያጉረጠረጡ እንደገና አልኮል መገልበጥ ጀመሩ፡፡\ከትንሽ ጊዜ በኋላ ብርሃኑ ወሬውን ቅደድ ጀመረ፡፡ የኢህአፓን ከንቱነትና መፈረካከስ አመራሩን እየኮነነ ከዘላበደ በኋላ በሱ እምነት ደርግ ጋር ተጠግቶ በኢህአፓ ላይ ቀይ ሽብር ማፋፋም የወቅቱ አንገብጋቢ ጥያቄ መሆኑን ገለጸልኝ፡፡ አያይዞም የጩልሌ እምቢታ ምን እንዳመጣበት አበክሮ አሳሰበኝ፡፡ ላብ በላብ ሆኜ እየተብረከረኩ እምቢታዬን ገለጽኩለት፡፡ ብዙ ሊያግባባኝ ሞከረ፡፡ ምንም እንኳ በሁኔታው ብደናገጥና ብፈራም ፍንክች አላልኩለትም ነበር፡፡ በግልጽም ነገረኝ፡፡ በጨካኙ የደርግ ምርመራ ሹም በሻለቃ ብርሃኑ ከበደ ሥር እንደሚሰራና ብዙ የኢህአፓ ጓዶችን ወደ ደርግና ወደአብዮቱ እንዲመለስና እምቢተኞችም እንዳስመታ ገለጸልኝ፡፡ አሁን ተደናገጥኩ ፍርሃቴም ቀጠለ፡፡ ብርክ ያዘኝ ከህሊናየ ጋር እየተሟከትኩ ቡና ቤቱን ለቀቅን፡፡ መኪናዋ ወደ አራት ኪሎ አመራች፡፡ በመካከላችን ፀጥታ ሸፍኗል በመጨረሻም ሰተት ብላ ሚኒልክ ግቢ ገባች፡፡ ከመኪና ወረድን በእግራችን ትንሽ ከሄድን በኋላ አንድ በጩኸትና በለቅሶ የተሞላ ቤት በረንዳ ላይ አስቀመጡኝ፡፡ ከጥቂት ቆይታ በኋላ አንድ የሰከረ መርማሪ በጥፊ እያዳፉ አንዲት ጠባብ ክፍል ውስጥ አስገብቶ አግዳሚ እንጨት ላይ ገልብጦኝ፡፡ ወዲያውኑ አንዲት በደም የተጨማለቀች ኳስ ቢጤ አንስቶ ወደ አፌ ሊወትፍ ሲል ብርሃኑ ደቡር ብቅ አለና ስሙን ጠርቶ ቆይ አለው፡፡ በቅጽበታዊ ገለል ብሎ ቆመ፡፡ ከሁኔታው ደቡር አለቃው መሆኑን ተረዳሁ፡፡ ‹‹እሱን ለኔ ተወው›› በማለት ከመጀመሪያው ጥፊ በቀር ተገልብጦ አዳነኝ፡፡ ብርሃኑ ደቡር ጓደኛዬን ማመን አቃተኝ የአብሮ አደግነት ቆሌ ከሰባተኛ ተነስታ መርካቶን ፒያሳን  ቤተመንግስት ገብታ አዳነችኝ፡፡ ክብር ምስጋና ይግባትና ከዚያ በኋላ አንድ በእስረኞች የተጣበበች ግማት በግማት ክፍል ውስጥ አጎሮኝ ተሰወረ፡፡ እዚያች ጠባብ ግም ክፍል ውጥ የሚዘገንኑ ትርኢቶች አጋጠመኝ አንድ ሁለቱ አዲስ ግርፎች ስለነበሩ ነባር እስረኞች ቁስላቸውን በቆሻሻ  ጨርቅ ሲጠርጉና ሲሸፍኑላቸው ተመለከትኩ፡፡ ቁስለኞቹም የስቃይ ድምጽና ለቅሶ ሲያሰሙ ታዘብኩ፡፡ በአጠቃላይ ሀያ ከሚሆኑ እስረኞች መሀል ሳልገረፍ የገባሁት እኔ ብቻ ነበርኩ፡፡ አይ! የመርካቶዋ አድባር ቆሌ! ሺህ አድባር ውለታሽን ይክፈሉሽ አልኩ በልቤ፡፡ እዚያች ክፍል ውስጥ ሳለሁ ከተመለከትኩት አዲስ ቁስለኛ ሲመጣ የከረመው ወደ ሌላ ቦታ ይወሰዳል፡፡ ማገገሚያ ጣቢያ አይነት ነበረችና አንዳንዴም ባሳቻ ሰዓት የተወሰኑ ሰዎች ይወስዳሉ፡፡ ዕጣ ፋንታየ ምን እንደሆነ ሳላውቅ ይኸው አስር ቀን ሆነኝ፡፡ በአስራ አንደኛው ቀን ሰባት የምንሆን እስረኞች ስማችን እየተጠራ እንድንወጣ ተደረገ፡፡ ምን ይሆን እያልኩ ስጨነቅ ከሌላ ቦታ ከመጡ አምሳ ከሚሆኑ እስረኞች ጋር በአንድ አዳራሽ ውስጥ ተደባለቅን ከጥቂት ጊዜ በኋላ የስብሰባው አስተናባሪ የዕለቱን አንቂና ተናጋሪ በአንዲት በር በኩል አስከትሎት ገባ፡፡ ሌሎች ይወቁት አይወቁት እንጃ እኔ ግን ጓደኛየን ደቡርን ሳየው ስላላስገረፈኝ ከልቤ እያመስገንኩ የሚለውን ለመስማት በጉጉት መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ ከንግግሩ ምንም የተለየ ነገር አልሰማሁም ያው እንደለመደው ኢህአፓን አጥብቆ አወገዘ ወደ አብዮቱ ካምፕ መመለስን አበክሮ ከአስገነዘበ በኋላ ምርምራችን ተጣርቶ ንጹህነታችን ስለተረጋገጠ ምህረት እንደተደረገልንና ከአሁን በኋላ ሰላማዊ ኑሮ እንድንጀምር አበክሮ ከአሳሰበን በኋላ ወዲያውኑ በተነን፡፡ ከደስታ ብዛት ግማሹ ያለቅሳል ሌላው ይስቃል አንዳንዱ ደግሞ የድጋፍ መፈክር ያሰማል ሳይጠየቅ ታዲያ ሌላ ምን ያድርግ? አይ የነፍስ ነገር የሆነው ሆኖ ከአዳራሹ ስንወጣ ደቡር ወደ ቢሮው ወሰደኝና ጥቂት ምክር ከሰጠኝ በኋላ ለታክሲና ለምግብ የሚሆን አስር ብር ሰጥቶኝ እንድሰወር ነገረኝ፡፡ አይ አብሮ ማደግ እያልኩ አመስግኘው ተለያየን፡፡

ህቡዕ በነበርኩበት ጊዜ ሁሉን ነገር በሬዲዮና በጋዜጣ እከታተል ነበር፡፡ በተለይም በ1968 እና በ1969 ኢህአፓ በከተማ ውስጥ በመደምሰሱ መኢሶንም ፍርጠጣውን ተያይዞት ስለነበር፤ ደርግ በነበረበት ፍልሚያ የውስጥ ተቀናቃኞችን መደምሰስና ማስወገድ ነበር፡፡ ባልታሰበ ሁኔታ ሰናይ ልኬና ኮሌኔል ዳንኤል አስፋው በሻለቃ ዩሃንስ እንደተገደሉ የወዝ ሊግ መዋቅር ከመቅጽበት ፍርስርሱ ወጣ፡፡ በወቅቱ በተራ ካድሬዎች ቀርቶ በራሳቸው በደርግ አባላት የሚፈራው ሻለቃ ብርሃኑ ከበደ የብርሃኑ ደቡርና የሌሎቹ መርማሪ ነፍስ ገዳዮች አለቃ ከወዝ አደር ሊግ መፈራረስ በኋላ ባንዲራው በመውደቁ ያ ጨካኝ አውሬ ነፍስ በላ በደርግ የመረሸን ፅዋ ደረሰው፡፡

በሁኔታው የተደናገጡት የወዝ ሊግ አመራር አባላት ይቅርታ እየጠየቁ ለመንግስቱ ሀይለማርያም ገበሩ በተዋረዱም ብርሃኑ ደቡርና መሰል ጓደኞቹ አለቃቸውን ሻለቃ ብርሃኑ ከበደን እየኮነኑና እያወገዙ ነጻ ሆኑ የዛን ጊዜዎቹ ጲላጦሶች! ደቡር ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ጠፋ፡፡ እንደ እኔ ህቡዕ ገባ ወይስ ከአገር ወጣ እያልኩ አብሰለስል ነበር፡፡

ከወራቶች በኋላ የዳምጤ ልጅ ደቡር የሰደን ካባ ለብሶ ከፍተኛ ካድሬነት መከሰቱ ሰማሁ፡፡ ‹‹ለሆዳም በሬ ጭድ ያዝለታል›› እንዲሉ ብዙ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በሚካሄድበት ፒያሳ አካባቢ ነበር የተመደበው፡፡ እሳቱ ደቡር በስልጣኑ በመመካትና በማስፈራራት ብዙ ገንዘብ ዘርፏል፡፡ በነፃ ከሚጠጣውና ከሚመገበው ባሻገር በጣም የሚያሳዝነው እሱና ግብረ አበሮቹ በፀረ አብዮት ሰበብ ብዙ ወጣት ልጃገረዶችን እያሰሩ ደፍረዋል፣ አበላሽተዋል፡፡ በርብርቦሽ አባት አልባ ልጆችን አስወልደዋል፡፡ የርብርቦሽ ዲቃላዎች ማሳደግ አቅቷቸዋል፡፡ ብርሃኑ ደቡር በየሆቴሉ እየገባ በነፃ መብላትና መጠጣት መብቱ አድርጎት ነበር፡፡ ካስቴሊ በነፃ ይመግበውና ያጠጣው ነበር፡፡ ከምግብ ሁሉ ጥሬ ሥጋ አብልጦ ስለሚወድ በአራዳ ልኳንዳ ቤቶች በነፃ ትኩስ ብልቶች መብላት ሥራው ነበር፡፡ ሆዳም! ይህም ድርጊቱ የአደባባይ ምስጢር እየሆነ በመምጣቱ በቀንደኛው ደርግ አባልና የሰደድ የበላይ አካል በጋሻው አታላይ ክትትል እንዲደረግበት ታዘዘ፡፡ ክትትሉ ውጤት አስገኘ ኮንትኔንታል ቡና ቤት አጠገብ ወደ እርይ በከንቱ መውረጃ ላይ ፒዜሪያ የምትባል የጣሊያን ምግብ ቤት አለች፡፡ ጣልያናዊው ባለቤት ከለውጡ በኋላ ለላብ አደሮቹ መርቆ አገር ለቆ ሄደ፡፡ ላብአደሮቹ ለጥቂት ጊዜ አብረው ከሠሩ በኋላ በስምምነት ኤርትራዊ ላብአደር ምግብ ቤቱን ጠቅልለው ይህ ሰው በአካባቢው ቀበሌ ተመራጮች በፈለጉት ጊዜ መጥተው በነፃ ይመገቡ ጀመር፡፡ በተጨማሪም ገንዘብ ያስገብሩት ነበር፡፡ ችግሩን መሸከም ሲያቅተው በሰዎች ምክር አቤቱታውን ለከፍተኛው ካድሬ አሰማ፡፡ ደቡር አጋጣሚውን በጣም ወደደው፡፡ ቀበሌዎችን አስፈራርቶ ዘረፋውን አስቆመ፡፡ በምትኩ ቀበሌዎቹን ተክቶ በተራው ምግብ መጠጥና ገንዘብ መብላትና መጠጣት መዝረፍ ጀመረ፡፡

ይህ ሲሆን የቀበሌ ተመራጮቹ አልተኙለትም ነበር፡፡ ብዙ ጭብጥ መረጃዎች አጠናቅረው ለበጋሻው አታላዩ አቀረቡለት፡፡ የዳምጤ ልጅ እንደለመደው ፒዜሪያ ገብቶ ሰዎች ጋብዞ እየበላና እየጠጣ ተዝናንቶ ሲወጣ እጅ ወደላይ ተብሎ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ በማግስቱ በኢትዮጵያ ሬዲዮ ሆዳሙ ካድሬ ብርሃኑ ዳምጤ በሚል መግለጫ ግፉና ድርጊቱ ተነበበ፡፡ ከጥቂት ወራቶች እስር በኋላ በምህረት ተፈታ እስሩን አላከረሩበትም፡፡ ሁሉም ካድሬዎች የሱ አይነት ድርጊት  ይፈጽሙ ስለነበር፡፡ ከተፈታ በኋላ በአንዳንድ ጓደኞቹ እርዳታ ግብርና ሚኒስቴር ተቀጥሮ አጋርፋ እርሻ ማዕከል ተመደበ፡፡ እዚያ እየሰራ ሳለ እንደገና ታሰረ ምክንያቱን አላውቅም፡፡ በብዙ አማላጅና በሚኒስትሩ በዶክተር ገረመው ደበሌ ግፊት በእስር ተፈትቶ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ፡፡ በወቅቱ ደርግ በመላው ምስራቅ አውሮፓ ኮሚኒስት አገሮች የፖለቲካ ስልጠና እንዲገኙ ካድሬዎችን ይልክ ነበር፡፡ ታዲያ ቀልጣፋው ብርሃኑ ደቡር ተሰባብሮ ከአንድ ቡድን ጋር ወደሶቭየት ዩኒየን ለአስር ወራቶች የፖለቲካ ትምህር ተላከ፡፡ ከትምህርት መልስ ግብርና ሚኒስትር ተመለሰ፡፡ ሥራውን ጀመረ፡፡ ትንሽ ሰንበት ብሎ ወደ ዋናው ግብርና ሚኒስቴር ዕቃ ግዢ ክፍል ተመድበ፡፡ በመሆኑም ለሆዳሙ ጓደኛዬ ደቡር ሌላ አመቺ የዝርፊያ ሁኔታ ፈጠረለት፡፡ ከነጋዴዎች ጋር በመስማማት ገንዘብ ማካበት ጀመረ፡፡ ምርጥ ምርጥ ልብሶችና ጫማዎች መቀያየር ጀመረ፡፡ ቀን በቀን በውስኪ መታጠብ ጀመረ፡፡ በ247 ብር ደሞዝ ደርግ ድንብርብር ባለበት ዘመን ብዙ ፕሮግራሞ ያወጣ ነበር፡፡ በዚህም መሠረት የኢሠፓን ካድሬዎች ለልማትና ለመንደር ምስረታ በሚል በየክፍለሀገሩ በተበተነበት ጊዜ ብርሃኑ ወደ ጎጃም ክፍለ ሀገር ዘመተ፡፡ ተልዕኮውን ጨርሶ ሲመለስ አጅሬ ደቡር ‹‹ምን ይገደው›› ተገለባብጦ የኢሰፓ የአባልነት ቀይ ደብተር እጁ ውስጥ አስገባ፡፡ በዚህም ቀይ ደብተር ብዙ ነገደበት፡፡ ዘረፈበት ሌላም ሌላም ብዙ አደረገበት፡፡ ትዝ ከሚሉኝ አንዱ የግርማ ቢራቱ ነገር ነበር፡፡ ግርማ ቢራቱ የአባቱን ንግድ መርካቶ ውስጥ ያካሂዱ ነበር፡፡ ደስተኛ፣ ተጫዋች ሴት አሳዳጁና መጠጥ ወዳጁ ግርማ በጊዜው ተገጥሞለት ነበር

‹‹ከሰው ግርማ ቢራቱ

ከመኪና ቶዮታ ማርክ ቱ››

የዘመኑ የመርካቶና የአራዳ ልጆች ያስታውሱታል ብዮ አምናለሁ፡፡ ሞቷል ነፍሱን ይማረውና ታዲያ የብርሃኑ የገንዘብ ምንጭ ሆኖ ነበር፡፡ ወዶ ሳይሆን በመፍራት ሌሎች የሰፈራችን ነጋዴዎችና የቡና ቤት ሴት ባለቤቶች ገንዘብና ሩካቤ ስጋ ይለግሱት ነበር፡፡ ሳይወዱ በፍርሃት የደቡር ጉዞ ሁሌ እንደቀጠለ ነው፡፡ በተለመደው ‹‹አፍዝ አደንግዝ›› በነያሬድና በነአሳየ ብርሃኑ አማካይነት ደስ አለኝ ቤዛን ገልብጦ የግብርና ሚኒስቴር ቋሚ ካድሬ ሆነ፡፡ ደሞዙን ከ247 ብር ወደ 710 ተወረወረ ‹‹የባለ ማስትሬት›› ደሞዝ!!! ዶ/ር ገረመውን እያጫወተና እያሳቀ እንዳያፈናቅለው አደረገ፡፡ ይህም ሽፋን በዶክተሩ ስም እየነገደ ጉቦ መቀበል እንዲችል ረዳው፡፡ የግብርና ሚኒስቴርን የፋይናንስ መምሪያ ሃላፊዎች ብዙ ያልተወራረደ ገንዘብ እንዳለበት ተረጋግጦ እያለ እንዲመልስ አልተጠየቀም ካላበደ በቀር ማን ደፍሮ ሊጠይቅ! የብርሃኑ ዝርፊያ ብዙ አይነት ነበር፡፡ በብዙ መቶዎች የሚያስተናግደውን የሰራተኞች ክበብ መሪዎቹን አባሮ ክበቡን በቁጥጥሩ ሥራ ካደረገ በኋላ ከመርካቶ (ከሰፈሩ ሰባተኛ) ጩልሌ ልጆች ቀጥሮ የክበቡን ገቢ እየሰነጠቀ ሙልጭ አርጎ በልቷል፡፡ ሲሾም ያልበላ አይነት! ለምንስ አይዘርፍ ማን ሊጠይቀው! እንደገና ደርግ ሊወድቅ በሚንገዳገድበት ጊዜ የሞት የሽረቱን የኢትዮጵያን ወጣቶች እያስገደደ ለብሄራዊ ውትድርና ይመለምል ነበር፡፡ ካድሬዎች በየቀጠናው ኢሰፓ አንደኛ ፀሐፊዎች አመራር በኮሚቴ ምልመላውን ተያይዘውት ነበር፡፡ ብርሃኑ ደርቡም የአንዱ ቀጠና ኮሚቴ አባል ነበር፡፡ በወቅቱም ሀብታሞች ልጆቻቸው እንዳይዘምቱባቸው ለአንድ ልጅ እስከ 2000 ብር ይከፍሉ ነበር፡፡ እያንዳንዳቸው ቀጠናም የተወሰነ ኮታ መምታት ስለነበረበት ጉቦውን ከበሉ በኋላ በምትካቸው የድሃ ልጆችንና የጎዳና ተዳዳሪዎችን እያፈሱ ኮታቸውን ያሟሉ ነበር፡፡ ደቡርና መሰል ጓደኞቹ!

ብርሃኑ ደቦር የዳምጤ ልጅ ይሁን አባ መላ ምን ያላደረገው ነገር አለ፡፡ በስልጣኑ በመጠቀም መሬት ተመርቶ ጉለሌ ጳውሎስ ሆስፒታል ጀርባ ቪላ ቤት መሥራት ጀመረ፡፡ ቤቱም በሚያስደንቅ ሁኔታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገባደደ፡፡ አያስገርምም፡፡ ጥሬ እቃዎቹ በሙሉ የተበረከቱት በልዩ ልዩ ነጋዴዎች ሲሆን መሃንዲዎቹና እንጨት ማገሩን የግብርና ሚኒስቴር ነበሩ፡፡ በነገራችን ላይ አምፑል እንኳን ከኪሱ አውጥቶ አልገዛም፡፡ ምላጩ ደቡር አባመላ በዚህ አላበቃም ቤት መሸጥ መለወጥ በተከለከለበት ዘመን አንድ ቀን እንኳ ያላደረበት ቤት ጠግሮ ዶላሩን አጥቁሮ ማንም ሳይሰማ ሽል ብሎ አሜሪካ ገባ፡፡

ያ ተበድሮ ያላወራረደው ገንዘብ በግብርና ሚኒስቴር የፋይናንስ ሰራተኞች ደመወዝ እየተቆረጠ ለመስሪያ ቤት ገቢ ተደረገ ‹‹አይጥ በበላ ዳዋ ተመታ›› አይነት!

ከላይ የብርሃኑ የዘር አመጣጥ የጠቀስኩት ያለ ምክንያት አልነበረም፡፡ ብርሃኑ የቀንደኛው ወያኔ ግልገል የግርማ ብሩ የአክስት ልጅ ነው፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ ለግርማ ብሩ አጎቱ ነው፡፡ በግርማ ወልደጊዮርጊስ ልጀምር ይቅርታ በአክብሮት ባለመጥራቴ አክብሮት አይገባውምና! ይህ ሰው ሁለት ዘመን እያምታታና እያጭበረበረ የኖረ ሲሆን አሁን በሶስተኛው መንግስት ፕሬዚዳንት ሆነ፡፡ በንጉሱ ዘመን የፓርላማ አባልነቱን ወደ ኋላ ትቼ በደርግ ጊዜ የፈፀማቸውን ድርጊቶች ላውሳ፡፡ የኤርትራ ክፍለ ሀገር ሲቪልአቪየሽን ሀላፊ ሆኖ ተሾመ፡፡ ከጥቂት አገልግሎት በኋላ በይዘቱም ይሁን በቅርፁ ከርሳሙ መቶ አለቃ ግርማ ተስባብሮ የኤርትራ የትራንስፖርት አላፊ ለመሆን በቃ ቦታውን የፈለገው ያለ ምክንያት አልነበረም፡፡ ‹‹ቦታው የወርቅ ማዕድን ነበርና›› በወቅቱ በደርግ አሰቃቂ ግፍ ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ኤርትራውያን ንብረታቸውን እየተው ሀገራቸውን ጥለው ወደ ውጪ ሀገር ወይም ወደበረሃ የሚጠፋበት ጊዜ ነበር፡፡ ምስኪኖች ሞትን ፈርተው! ‹‹ቀልጣፋው›› መቶ አለቃ ግርማ የየብሱና የባህሩ ትራንስፖርት ሀላፊው በመሆኑ የኤርትራውያኑን ምርጥ ምርጥ መኪናዎች ከምጽዋ አሰብ እየላከ በልጁ በሰለሞን ግርማ አማካኝነት አዲስ አበባ መሃል አገር እየቸበቸበ ብዙ ገንዘብ ካዝናው ውስጥ አስገብቷል፡፡ ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በልጁ ስም አንድ የንግድ ድርጅት አቋቁሞ ከሩቅ ምስራቅ የተዋጊ አውሮፕላኖችን መለዋወጫ የአውሮፕላን ቦንቦችና ሌላም ነገሮች መንግስት በማቅረብ ከፍተኛ ገንዘብ በኮሚሽን አግኝቷል፡፡ ‹‹ወያኔ እንደገባ በመገናኛ አውታሮች ሰለሞን ግርማ በወንጀል እንደሚፈለግ የለፈፈውን ያጤኗል እንደ አባት እንደልጅ እንዲሉ›› ሰለሞን ተቀለጣጥፎ ሩቅ ምስራቅ ኮበለለ፡፡ አሁን የት እንዳለ አላውቅም፡፡ መቶ አለቃ ግርማ ይበልጥ የሚታወቀው በስነ ምግባር ብልሹነቱና በሴሰኝነቱ ሲሆን የአስራ አራትና የአስራ አምስት እድሜ ያላቸውን ወጣቶች በሌሊት ሶስትና አራቱን እያበላሸ ያድር እንደነበር ይታወቃል፡፡

ለምሳሌ ያህል ከሁለት ወጣት እህትማማቾች ልጆች ማስወለዱም ይታወቃል፡፡ አብረኸት የተሰኘችውን የ12ኛ ክፍል ውሽማውን የምጽዋ ትራንስፖርት ሃላፊ በማድረግ የምሁራን ሠራተኞችን ሞራል አዳሽቋል ከርሳሙ መቶ አለቃ ግርማ የአሁኑ ፕሬዚዳንት! ያች ልጅ ‹‹Suger Dady›› ብላ የፃፈቸውን ያጤኗል፡፡

ግርማ ብሩን በተመለከተ ጎበዝ የቀለም ተማሪና በጣም ቀዝቃዛ ሰው ነበር፡፡ ከአብዮቱ ፍንዳታ በኋላ በኢህአፓነት ተጠርጥሮ ደብረዘይት ከተማ ታስሮ ሲያበቃ የተፈታ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲውን ከጨረሰ በኋላ አንገቱን ደፍቶ በሚኒስቴር መስሪያ ቤት ተቀጥሮ ወንበር ያሞቅ ነበር፡፡ ወያኔ ከገባ በኋላ ከአጎቱ ከግርማ (መቶ አለቃ) ጋር በመሆን የሶዶ ጅዳ ተወካይ በመሆን ተሽሎክልኮ ባልዋለበት የኦህዴድ አባል በመሆን እስከ ሚኒስቴርነት ደረሰ፡፡ ይህ የድንጋይ ስር እባብ ምን ያህል ጨቋኝ አድርባይ ስለመሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ነውና ብዙ አልዘበዝብም፡፡ ለመሆኑ እነዚህ ሶስት ዘመዳም ጉዶች አጋምጃን ይወክላሉ? የባልቻ አባ ነፍሶ አገር እነዚህን ጎዶች ታብቅል? ባልቻ አባ ነፍሶስ ምን ይሰማው ይሆን መልሱን ለአባ  ነፍሶ አፅም ትቸዋለሁ፡፡

በቸር ይግጠመን

መስፍን ቀጮ/ወፍ

ከጠቅላይ ቢሮ አዲስ አበባ

 

 

ሙክታር ከድርና የኦሮሞ አክራሪዎች –ናኦሚን በጋሻዉ !

$
0
0

ናኦሚን በጋሻዉ !

Muktar-Kedir1

ሙክታር ከድር

እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ሆነው አገልግሏል። አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ ትልቅ ክልል የምትባለው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘዳነት ሆኗል። ሙክታር ከድር ይባላል። የኢህአዴግ አንዱ  የሆነው የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክርሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር ነው።

ከአዲስ አበባ ደቡብ ምስራቅ 150 ኪሎሜትር ርቃ በምትገኝ ሄቶሳ በምትባል የአሩሲ መንደር አንድ ትልቅ ግንባታ ለማስመረቅ በክብር እንግድነት ይገኛል። አንድ ወንዝ ተገድቦ፣ ወይንም የጤና ጣቢያ፣ ትምህርት ቤት ተሰርቶ ለመመረቅ አይደለም የመጡት። እልም ባለ ገጠር መሃከል፣ አካባቢዉ ሁሉ ሜዳና እርሻ በሆነበት ቦታ፣ አንድ ትልቅ በአይነቱም፣ በይዘቱም የተለየ፣  ፈረንጆን እንደሚሉት ዊርድ የሆነ ሃዉልት ቆሟል። የአኖሌ ሃዉልት ይሉታል።

በቀድሞ ጊዜ በገዳ ስራአት ጀግና የነበሩ የኦሮሞ መኮንኖችን  ገድል የሚዘክር፣ ወይም በቅርብ ታሪካችን እንደ አብዲሳ አጋ፣ ባልቻ አባ ነፍሶ የተሰኙ የኦሮሞ ጀግኖችን የሚያሳይ ሃዉልት ቢሆን ሸጋ ነበር። ነገር ግን ሃዉልቱ ጡት የያዘ አንድ እጅን ያሳያል። ከመቶ አመት በፊት የሚኒሊክ ወታደሮች የአርሲ ኦሮሞዎችን ጡት ቆርጠዋል የሚሉትን የሌለ የፌጥራ አፈታሪክ ለማስታወስ ነዉ ብለው የቆሙት ሃዉልት። ያዉ በሚሊዮኖች በሚቆጠር ከሕዝብ ካዝና በተወሰደ ብር የተሰራ ሃዉልት። «አማራዎች እንደዚህ ጡት ቆራጮች ናቸው!» የሚለው የጥላቻ መልእክት በኦሮሞ ወጣቶች ላይ ከልጅነታቸው ጀምሮ ለማስረጽ ሆን ተብሎ የቆመ ሃዉልት። ኦሮሞው አማራዉን እንዲጠላ፣ እንድ እፍልስጤምና እስራኤል በመሃከላቸው ግድግድ ተፈጥሮ  እንዳይተማመኑ  እንዲተላለቁ ለማድረግ የቆመ ሃዉልት። የሰይጣን የዲያብሎስ ሃዉልት!!!

በአኖሌ በአጼ ሚኒሊክ ወታደሮች ተደረገ የተባለው  ጡት ቆረጣ መደረጉን የሚያረጋግጥ ምን አይነት የጽሁፍ መረጃ የለም። ዶር ነጋሶ ጊዳዳ በፓልቶክ ሲጠየቁ «ምንም አይነት የጽሁፍ ማስረጃ የለም፤ ግን በአፈ ታሪክ ነው የተላለፈው» ነበር ያሉት። የአጼ ሚኒሊክ ወታደሮች አያታቸውን አስረዉ ወፍጮ እንዲፈጩ ማስገደዳቸዉን የተናገሩት ዶር ነጋሶ ፣ በወለጋ የሚኒሊክ ወታደሮች ጡት ቆርጠው እንደሆነ ሲጠየቁ «ወለጋ እንደዝያ አልሆነም» ነበር መልሳቸው። አጼ ሚኒሊክ በጎጃም በሃርረ፣ በወላይታ በበርካታ ቦታዎች ወታደሮቻቸው ልከው አስገብረዋል። በአርሲ ተደረገ ከሚባለው ማረጋገጫ ካልቀረበበት  አፈ ታሪክ ዉጭ በሌሎች ቦታዎች የጡት ቆረጣ ተደረገ የሚል በአፈ ታሪክም አልተሰማም።

እንግዲህ እንደዚህ ዉሸት የሆነን አፈታሪክ በማራገብ ፣ ት/ቤቶችና  ክሊኒኮች በመሳሰሉ ቁም ነገሮች ላይ ገንዘብ ከማጥፋት ይልቅ፣ ዘረኛዉና ጠባቡ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ይህ አይነቱን፣  ሕዝብን ከሕዝብ የሚያቃቅር፣ ዜጎችን ወደ እልህና ወደ ጦርነት እንዲሄዱ የሚገፋፋ፣ ጥላቻን በሰዎች ልብ ዉስጥ የሚዘራ፣  አሳዛኝና አስቀያሚ ሃዉልት ማቆሙ፣ ምን ያህል  ለአገር ጥቅም ሳይሆን ለአገር መጥፋት እየሰራ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።

እስቲ ወደ ሙክታር ከድር መልሼ ልዉሰዳችሁ። በቅርቡ ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣  በኦሮሚያ ዉስጥ የሚኖሩ ኦሮሞ ያልሆኑ ኢትዮጵያዉያንን በተመለከተ በኦህደድ ወንጀሎች ስለተሰሩ ግፎች ሲናገሩ፡

«I do know that there are Oromo individuals who do say “ non-Oromos  or those who do not speak Afan Oromo,  have no rights. They are second citizens.” I have expressed already that I am against such people. This brings me back to the OPDO “Gimgama” of 1989. OPDO was then confronted with serious problems of human rights violation, corruption and anti-democratic Oromo nationalism. We evaluated the leadership, the cadres and members of OPDO under the motto “Clean OPDO from OLF attitude (anti-democratic/narrow) and Naftagna (please note that Naftagna is not equal to Amhara) practices (violation of democratic and human rights including corruption). The result of the “Gimgama” was that thousands were found out to have anti-democratic attitudes and carried out Naftagna practices. 189 cadres were imprisoned so that they are brought to justice because of high corruption and serious human rights violation. Thousands were expelled because of their bad attitudes and bad practices. Only about 300 were kept after receiving warnings»  በማለት ነበር በኦህድድ አክራሪዎች የተፈጸሙትን ወንጀሎች የዘረዘሩት።

 

ማስጠንቀቂያ ተሰጧቸው ከነበሩ  አክራሪ ዘረኞች መካከል  ማን የሚገኝ  ይመስላቹሃል ? የአኖሌ የጥላቻ ሃዉልት መራቂ የሆነው ኦሮሚያን ኦሮሞ ካልሆኑት የማጽዳት አላማ በዉስጡ ያለው፣ የኢትዮጵያዉ  ጀነራል ምላዲቹ ፣ ሙክታር ከድር አንዱ ነበር።

«Among these were Alemayehu Atomsa and Muktar Kadir. Anyway, what was going on then was really very sad. Non-Oromo Ethiopian investors and traders were not welcome. Documents for bids for land were leaked out to Oromos so that they could win against non Oromo (for example against the 7 rich Gurage in Jimma). Shops were closed down. Boards to guide people were written only Qube (no Amharic and English translation). Appeal documents written in Amharic were rejected. Schools refused to give lessons in Amharic. (With silly arguments “we were formally forced to learn in Amharic, now it is their turn to be forced to learn in Afan Oromo.) We will not pay money for Amharic teachers and books”). Unfortunately, I hear that the attitude and practice still lingers.» ይላሉ ዶር ነጋሶ በጽሁፋቸው።

ታዲያ የሙከታር ከድር ዘረኛና የጥላቻ ታሪክ እየታወቀ፣ የኦሮሚያ ፕሬዘዳንት  ማድረጉ፣ የአኖሌን የጥላቻ ሃዉልት ማቆሙ፣  ኦሮሞዉን ለመጥቀም ነው ወይንስ ኦሮሞውን ከሌላ ህዝብ ጋር ለማጋጨት ?  ኦሮሞው ከሌላው ሕዝብ ጋር የተዛመደ፣ የተዋለደ፣ የተሳሰር አይደለምን ? ለዲሞክራሲ ቆመናል የሚሉት፣ የኦሮሞ ድርጅት መሪዎችስ ይሄን የነሙክታር ከድር መርዝ ማዉገዝ የለባቸውምን ?  ለኦሮሞው ከአማራዉ፣ ከጉራጌዉ፣ ከጉሙዙ፣ ከቡርጂዉ፣ ከሲዳማው፣ ከጌዴዎው፣ ከሶማሌው ጋር አብሮ ተከባብሮ፣ ተስማማቶ መኖር አይሻለዉምን ? ለምንስ  እነዚህ አካራሪ ኦሮሞዎች ጠብ ይፈልጋሉ ? ለምን ተነጥለው ለመታየት ይሞክራሉ ? የሚያስተሳሰር፣ የሚያቀራራብ፣ አንድ የሚደርግን ማብዛትና ማስፋፋት እንጂ የሚያጣላና የሚያቃቅር ነገር ለምን እንጭራለን ?

አክራሪዎች በአኖሌ እንዳየነው አይነት ካከረሩ፣ ኦሮሞ ለኦሮሞዎች በሚል፣ ባለፈበትና በማይሰራ ባዶ ፉከር ከተነሱ፣  በዚያኛዉ ወገን ያሉት ተመሳሳይ እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ ዘነጉትን? ወይስ «በዙሪያችን ካሉ ሌሎች ሕዝቦች እዚያ ማዶ ያለው የትግሬ ጦር ይጠብቀናል» የሚል ግምት አላቸው ? እነዚህ አክራሪ ኦሮሞዎች ሰው ዝም ሲላቸው ትንሽ ልባቸው ያበጠ መሰለኝ። አላወቁትም እንጂ፣  እንዲሁ በባዶ ባበዱ ቁጥር እራሳቸዉን ነው የሚያስገምቱት። አለም በግሎባላይዜሽን በተሳሰረችበት ዘመን፣ ምን ያህል ኋላ ቀሮች መሆናቸዉን ነው የሚያሳዩት።

 

እንግዲህ ልብ ይገዙ ዘንድ እመክራቸዋለሁ። ጥላቻ ለማንም አይጠቅም። እልህ ለማንም አይጠቅምም። ዘረኝነት ለማንም አይጠቅምም።

 

 

በዘሀበሻ ላይ የወጣውን የቅዳሜ ዕለት የደብረሰላም መድሐኒአለም ውሎ ተከታትዬ በጣም አዘንኩኝ (ታዛቢ)

$
0
0

debereselam Minnesotaበሚኒሶታ መድሐኒአለም ታሪክም ላይ ጥቁር ነጥብ ጥሎ ያለፈ እለት መሆኑንም ነው የተረዳሁት። የሚኒሶታ መደሐኒአለምን ቤተክርስቲያንን ውዝግብ በቅርብ ሆኜ የምከታተል አባል በመሆኔም ባለፉት 15 አመታት የመጡትን የሄዱትን የወረዱትን ጠንቅቄ አውቃለሁ በተለይም ባለፈው 1 አመት  ከ 6 ወራት ውስጥ ያለውን ሒደት።ለዛሬው ብዙም ወደ ዋንኛው ችግር ጠልቄ ገብቼ ባልናገርም ነገር ግን ቤተክርስቲያኗ በአጣብቂኝ መንገድ ላይ እንዳለች ሁላችንም የምናውቀው ነው። የወደፊቱን አቅጣጫ ለመወሰን የሁለቱም ጎራ የተሰለፉት ጉዳያቸውን  በፍርድቤት አሲዘው ለ ሜ 11 ቀን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲጠራ ቀጠሮ መያዙን ወቅታዊው ሊቀመንበር በቤተመቅደሰ ፈትለፈት ቆመው 20 ቀናት በፊት ነግረውናል። –- ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ—

የኦሮሚያ ልዩ ዞኖችን በሚያጠቃልለው ማስተር ፕላን ላይ መግባባት አልተቻለም

$
0
0

ታምሩ ጽጌ

740px-Oromia_in_Ethiopia.svg-በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ማስተር ፕላኑን ተቃወሙ

-ከአዲስ አበባ አዳማ በአዲሱ መንገድ ግራና ቀኝ መሬት መሸጥ ቁጥጥር ሊደረግበት ነው

አዲስ አበባ ከተማና በዙሪያዋ የሚገኙትን አምስት ልዩ የአሮሚያ ዞን ከተሞች ሰበታ፣ ቡራዩ፣ ሱሉልታ፣ ለገጣፎና ገላን አጠቃሎ በተሠራው ማስተር ፕላን ላይ መግባባት ባለመቻሉ ግምገማዊ ውይይት በማድረግ የመግባቢያ ፊርማ ለማድረግ የተጀመረው ስብሰባ ሳይጠናቀቅ መቋረጡን ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

መጋቢት 19 ቀን 2006 ዓ.ም. የልዩ ዞኑና የአዲስ አበባ ከተማ ተወካዮች በማስተር ፕላኑ አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት የተሰበሰቡ ቢሆንም፣ በተሠራው ማስተር ፕላን ላይ አንድ ዓይነት አቋም ሊይዙ አለመቻላቸው ታውቋል፡፡ ከአንዳንድ ተሳታፊዎች መግባባቱን ወደኋላ ሊመልሱ የሚችሉ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በመነሳታቸው፣ በዕለቱ ይካሄዳል ተብሎ በነበረው የጋራ ውይይት ላይ ልዩነት መፈጠሩን ምንጮች አስረድተዋል፡፡

በአዳማ በተደረገው ውይይት በልዩ ዞኖቹ በኩል የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አብዱልአዚዝ መሐመድና አዲስ አበባን በመወከል ከንቲባ ድሪባ ኩማ በጋራ ውይይቱን የመሩት ቢሆንም፣ በውይይቱ የተሳተፉ የተለያዩ ቢሮ ኃላፊዎችና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ባነሱዋቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምክንያት በዕለቱ ሊቋጭ ዕቅድ ተይዞለት የነበረው ግምገማዊ ውይይት ለሌላ ጊዜ መተላለፉን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን መሠረት ያደረገ የጋራ ማስተር ፕላን አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት፣ የአዲስ አበባና ዙሪያዋ ኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ልማት ፕላን ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ተቋቁሞ፣ ከስምንት ዓመታት በላይ ጥናትና ውይይት ከተደረገበት በኋላ፣ ማስተር ፕላኑ ተሠርቶ መጠናቀቁንና በመጪው ግንቦት ወር ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቅ ነበር፡፡

ፕሮጀክቱ በ1996 ዓ.ም. በቀድሞው ከንቲባ አቶ ኩማ ደመቅሳ መጠንሰሱን የሚናገሩት ምንጮች፣ ለፕሮጀክቱ መጠንሰስ ዋና ምክንያት የሆነው በአዲስ አበባ ዙሪያ የሚገኙት የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች በኢኮኖሚ ተጠቃሚ አለመሆናቸውን ታሳቢ ያደረገ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡

በተሠራው ማስተር ፕላን ላይ ሁለቱ ወገኖች ተወያይተውና ተፈራርመው ለመለያየት በአዳማ ያደረጉት ስብሰባ በተለይ በአንዳንዶቹ የውይይቱ ተሳታፊዎች ያልተጠበቀ ጥያቄና አስተያየት ግራ የተጋቡት አቶ ድሪባ፣ ስብሰባውን ለመገናኛ ብዙኃን ዝግ በማድረግ ውይይቱን መቀጠላቸውን ምንጮች አስረድተዋል፡፡

ጥያቄዎቹና አስተያየቶቹ የተነሱት ከፍተኛ ኃላፊነት ላይ ባሉ ግለሰቦች በመሆኑ፣ ምናልባት ስለማስተር ፕላኑ በቂ ግንዛቤ እንዳልተፈጠረ በመገንዘብ እንደገና ግንዛቤ ለማስያዝ ስብሰባው በዝግ እንዲካሄድ ሳይደረግ እንዳልቀረ ምንጮች ግምታቸውን ተናግረዋል፡፡

ማስተር ፕላኑን በሚመለከት መጋቢት 19 ቀን 2006 ዓ.ም. አዳማ ላይ ተደርጎ የነበረው ግምገማዊ ውይይትና ይፈጸማል ተብሎ የነበረው የስምምነት ፊርማ ለምን እንደተቋረጠ ከሪፖርተር ጥያቄ የቀረበላቸው የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዳዊት ንጉሴ፣ ስብሰባው ተደርጎ እንደነበር አረጋግጠው፣ በወቅቱ መፈራረሙ የቀረው ስምምነት ጠፍቶ ሳይሆን፣ ለሁለት ቀናት ይደረጋል የተባለው ግምገማዊ ውይይት በአንድ ቀን እንዲያልቅ በመደረጉና ጊዜ ባለመብቃቱ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ማስተር ፕላኑ አዲስ በመሆኑ መረጃ የሚፈልጉ ወገኖች እንደነበሩና ጥያቄ ማንሳታቸውን የገለጹት አቶ ዳዊት፣ አንዳንድ ግለሰቦች፣ ‹‹አዲስ አበባ ኦሮሚያን አስፋፍታ ልትይዝ ነው፣ ወደ ኦሮሚያ ምድር ልትስፋፋ ነው፤›› የሚል የተሳሳተ ግንዛቤ መያዛቸው፣ ለጥያቄያቸው በቂ ምላሽ እንደተሰጣቸው ጠቁመዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በበላይ አመራሮችና በቦርድ የሚመራ በመሆኑ፣ በሁሉም ነገሮች ላይ ስምምነት ላይ ተደርሶ ፕሮጀክቱ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሆነና ምንም ዓይነት ችግርና አለመግባባት እንደሌለ አስረድተዋል፡፡

ልዩ ዞኖቹን ያጠቃለለውን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ የፓለቲካ ፓርቲዎች ተቃውመዋል፡፡ ፓርቲዎቹ በጋራ ባወጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ ‹‹ፊንፊኔ የኦሮሚያ ዋና ከተማ መሆኗ በሕገ መንግሥታችን ተደንግጎ እያለና በሕገ መንግሥት አንቀጽ 49(5) ላይ በጉልህ ኦሮሚያ ከፊንፊኔ አስተዳደር ልዩ ጥቅም ይከበርላታል በሚል ቢደነገግም፣ መንግሥት በተገላቢጦሽ በፊንፊኔ ዙሪያ ያሉትን ከተሞች በልማት ሰበብ በፊንፊኔ ሥር ለማዋል የሚያደርገው የረቀቀ ተንኮል ሕገ መንግሥቱን የሚስ ነው፤›› ብለዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የኦሮሞ ሕዝብ ሳይወያይበት፣ ሳይመክርበትና ምክንያቱን ሳይረዳ በሁለቱ ወገኖች ውሳኔ ብቻ መደረግ ስለሌለበት ድርጊቱ በአስቸኳይ እንዲቆምም ፓርቲዎቹ ጠይቀዋል፡፡

በማስተር ፕላኑ 85 በመቶ የሚሆነው መሬት ለግብርና የሚውል ሲሆን፣ 15 በመቶ የሚሆነው ለመኖርያ ቤት ግንባታ የሚውል ነው፡፡ በአጠቃላይ በማስተር ፕላኑ ክልል ውስጥ 13 ሚሊዮን ሕዝብ ይኖራል ተብሎ ሲገመት፣ ስምንት ሚሊዮኑ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ እንደሚኖሩ፣ በነበረው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን እስከ 55 ፎቅ ብቻ መገንባት ይቻላል የሚለው ተነስቶ ከዚያም በላይ መገንባት እንደሚቻል ታውቋል፡፡

ማስተር ፕላኑ የሚያቅፋቸውን ልዩ ዞኖች በተለይም ከአዲስ አበባ አዳማ በተሠራውና በቀጣይም በሚሠራው ዋና መንገድ (ኤክስፕረስ ዌይ) ግራና ቀኝ ያሉ መሬቶች በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ ሕገወጥ በሆነ መንገድ እየተቸበቸቡ መሆኑን ተከትሎ፣ ጥብቅ ቁጥጥር ለማድረግ መወሰኑን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አብዱልአዚዝ መሐመድ ትዕዛዝ ምንም ዓይነት የመሬት ሽያጭ በሕገወጥ መንገድ እንዳይካሄድ ለማድረግ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ ትዕዛዝ መተላለፉ ተገልጿል፡፡

 

Source: Ethiopian Reporter

ከምዕራብ ሸዋ ተፈናቅለው በፌዴሬሽኑ አፈ ጉባዔ አግባቢነት የተመለሱት ዜጎች መሬታቸውን በሃይል ተነጠቁ

$
0
0

geberewoch ethiopia
ከዳዊት ሰለሞን

ከሰላሳ የማያንሱ የምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ዳኖ ወረዳ ባጅላ ዳሌ ቀበሌ ገ/ማህበር ነዋሪዎች ‹‹ ወደ ክልላችሁ ተመለሱ ›› ተብለው መሬታቸውን ለመነጠቅ መቃረባቸውን ለማመልከት አዲስ አበባ በመምጣት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ካሳ ተ/ብርሃንን ካናገሩ በኋላ አፈ ጉባኤው ‹‹ወደ ቀዬአችሁ ተመለሱ እኔ ችግሩ እንዲፈታላችሁ አደርጋለሁ››በማለታቸው ገበሬዎቹ ወደ አምቦ መመለሳቸው አይዘነጋም፡፡

ወደ አምቦ የተመለሱትን ገበሬዎች የዞኑ ሃላፊዎችና የኦህዴድ ካድሬዎች ‹‹አዲስ አበባ በመሄድ ገመናችንን አጋለጣችሁ››በማለት ሲዝቱባቸው መቆየታቸውን ገልጸዋል፡፡ከትናንት ጀምሮም የታጠቁ ሚሊሻዎችን በማስከተል የቀበሌ ገ/ማህበሩ አመራሮች‹‹መሬታችንን ለቃችሁ ወደ መጣችሁበት ክልል ተመለሱ ››በማለታቸውና ገበሬዎቹ ‹‹ አንለቅም ከዚህ ውጪ አገር የለንም›› ቢሉም በመሳሪያ በማስፈራራት ከአካባቢው እንዲርቁ በማድረግ መሬቱን ለሚፈልጓቸው ሰዎች ማከፋፈላቸውንና ሊደበድቡንና ሊገድሉን ይችላሉ ብለው የሰጉ ገበሬዎችም ልጆቻቸውንና ባለቤቶቻቸውን በመያዝ ጫካ መደበቃቸውን በስልክ ከስፍራው ያናገርኳቸው ሰዎች ገልጸዋል፡፡ገበሬዎቹ ከዛሬ ሀያ ዓመት በፊት ከጎንደር አካባቢ ተፈናቅለው አሁን ለስደት በተዳረጉበት አካባቢ የሰፈሩ ነበሩ፡፡

ገበሬዎቹ ለአቤቱታ አዲስ አበባ መጥተው በነበረበት ወቅት ለምን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ጋር ሄዳችሁ ተብለው መታሰራቸው አይዘነጋም፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ ቁጥር 7


ኋላ የመጣ ዓይን አወጣ! (ጌታቸው ረዳ ኢትዮጵያን ሰማይ አዘጋጅ)

$
0
0
ጌታቸው ረዳ

ጌታቸው ረዳ

The first part of this commentary is been written in Amharic. Unfortunately, I deleted it by accident and my Amharic font program got corrupted. And had no option, but to replace it in English whatever memory I had in mind from the deleted portion. So, my apology to my readers for presenting the article half English and part also Amharic.

On 6 April, 2014, I was contacted by a friend via text to listen a Pal Talk room namely “Debtera Leaks Political Secrets of Ethiopia –Voice Room” edited by a lunatic, drunkard and annoying type by the name Bruk (Brook) where the Ethio- media Editor Abraha Belay was interviewed.

Unfortunately, I was not able to listen to it and asked another friend to record the interview for me. My friend responded “I stopped going there a long time a ago. it is not a place where test of maturity is conducted. Especially, the editor is self deluded and a noisy moron.”- said my friend.

Since, I was in a situation where unable to listen to the interview, after a little while, he called me back and decided to journey there to the room and recorded Abraha Belya’s interview. He sent me a limited part of the recoded interview, because he got there after almost at the end of the interview.

This room, ‘Debtera Leaks Political Secrets of Ethiopia –Voice Room’, which is administrated by a certain name ‘Buruk/Brook’ whom I (after listening to the recoded audio what he was referring to particular opposition like me and few of my friends with the same position regarding our view that (“Tigrayans as beneficiary of TPLF”) deem to be indeed a psycho. He referred as “extreme right wingers”.

How pathetic this noisy moron could referred as such for arguing our views which any normal mind can see that for the last 22 years, the rulers are Tigrayans and the investment, the Defense, the Diplomacy, the Airline, the bank, the business, the political power, the armament, the money, the mining, the land is all at the hand of “MAJORITY” Tigrayans from the top tycoon to the lower Tigrayan strata.

As far as I know the name ‘Buruk/Brook’ means blessing, however, the experience was closer to a curse based on his smearing against us.

Later after I came home, my friend chatted with me via a phone, that he was ready to ask the editor of the room and Abraha Belay with regard to his insult against those of us. It was also perfectly obvious to my friend that entering such room, meant entering a room full of sealed minded elements, and ‘apologies’ will be confronted with violent insult and some intimidation and endless nonsense rhetoric, including an admin that would continually victimize his opponents by red doting by blocking text and muting their voices. So, he decided to restrain himself from commenting or asking for the sake of waiting to record the interview for me.

Now, let me take you to Mr. Abraha Belay and Mr. Buruk short interview as a sample sent to me by a friend.

Before that, I like to escape what Abraha Belay had to say about Media and fairness and the father of the TPLF General Haylom Araya.

He talked few distorted story regarding the father of Haylom contrast with the father of Tedros Hagos (TPLF elite). But, failed to tell us, why Hayelom’s father was also in prison for over 10 years. I have no idea when, Tedros’s father was Awraja GeZZi in Shire (since I was born in Axum and grew up for certain period with a family in a deep village called Semema and also in Indasilasse capital city of Shire (walking from Semema by foot and stay week in the capital back to my home village on Friday evening) for schooling when I was a small boy, before I moved back again to Axum). All I know is he was not Awraja Gezzi, but Prince Mengesha’s secretary.

There were two other Shire Awraja Gezzi when I was a little boy as far as I remember. Perhaps could be. The point is why also did not tell us Hadush Araya’s (Hailom’s) father was in prison for so many years during that era. He tried to labeled Araya as ArbeNga and Hagos as Banda. I doubt the allegation was right. Anyway, let me move on to the other issue.

According to another witness which I will quote him at the end of my comment here, Balambaras Hagos (the same name and title as my mother’s grand father) and the all TPLF founders/leaders as the children of Nobles from Tigray. I will quote all of them by name later. I will send the audio evidence from Berhe Hagos from one of the Geza Tegaru admin (an ethno-centric room and directed by a fanatic Amhara hater a lady named “Hidiyat Raya”- remember she was the one said “Gojame are ZikiteNga, Idiot, Subhuman” and for the Gondere as ‘Telat’ ). Berhe told us in the audio “TPLF leaders are all children of nobles and feudal who are the other side copy of Ras Mengesha and the likes who were repressive feudal of Tigray. “Amhara was not our repressors but the Tigrayan feudal oligarchies and barons” said Berhe. Though Berhe is unpredictable, he is all the time fluctuating with no coherent ideology. But, at time, he has some valid points such as this one here.

The other issue is a waste of time to deal with his (Abraha Belya’s) “fair media” nonsense rhetoric he was talking about, as if he too is not one of the Diaspora pathetic media personality.

We have so many evidence for the last 8 or so years as editor of Ethiomedia- he is nothing but a click for the certain moron individuals (many of them hard line ethno- nationalist secessionists like Negasso, Bulcha and the rest of the criminal OLF goons) and certain white collar elites who are nothing but basket of naïve elites nick named “Doctor Zero-0) and the rest of religious Mujahedeens and Jawars.

I really do not want to go further, – it makes me so sick when I heard this fellow talking about fairness media. Let me omit his nonsense freedom of media and information rhetoric aside for another time.

Let me also escape what he said in regard to the question “who is ruling Tigray?” Few of us said yes, Eritreans are ruling our people and our country. But, it is not entirely true that only Eritreans are ruling Ethiopia/Tigray as Abraha Hagos seemed to response.

Tigrayans are in power. Not Eritreans. There are individuals with Eritrean blood, but, there is nothing we can do if they said they are Ethiopians. The fact the matter is, there are many Tigrayans also worst than Eritreans who advocate for Eritrea and also for blockage of our sea ports. The entire TPLF is crazily in love about Eritrea. These elements have been deluded by false propaganda pumped to their soft head through teachings of a sophisticated psychological subversion from Ethiopia’s enemies of all corners.

Though, there is some truth to it that there are Eritreans in power glued inside TPLF, let us also not confused the ethno nationalist of Weyane Tigray of Tigray origin are responsible group for every crime done. They are majority in number.

If the rulers are Eritreans, whose fault is this? Tigrayans or Eritreans? Is it not Tigrayans especially Abraha Belay’s community/Awaraja “May Chew” (Raya ena Azebo) who are crazily in love with Weyane Tigray to the extent majority of that Awaraja new born youth are named after Hayelom Araya? Common now!

I will deal about this next time. Majority followers/puppets of Weyane Tigray are currently from Enderta and MayChew Awraja.

We ask why the shift from አሽዓ (Axum, Shire, Adua) to those known hereditary rulers of Tigray feudal territories (Enderta and Raya) responsible for First Weyane (ቀዳማይ ወያነ) whom at this time population in particular the youth and the farmers are seen as fanatic supporter of Weyane Tigray?

We ask why the shift now, where these two Awraja were known for their melting pot and somewhat friendly society as good Ethiopians who tend to be somewhat neutral from being hardliner ethicist than the other Awraja before TPLF created. Thorough Research needs to be studied.

The Ethiomedia editor Mr. Abraha Belay also amazed me when he said “if there was a hero like Alemayohu who exposed the hidden secret of Meles Zenawi inside TPLF as Alemayohu exposed the hidden secret of the Shaabiya spy Tesfaye Gebreab- Ethiopia or TPLF; as organization or society of Tigray people would have not been hijacked by Eritreans to favor Eritreans”.

How premature, how silly one can be than this argument off line?

Meles Zenawi was not doing his subversive mission secretly as Abraha thought Meles was secretive. None of them did secretly. Including the Tigrayans in higher position or lower position. They wrote books, they argued, they openly intimidate, arrest, murdered anyone who do not accept the theory of colonialism by Ethiopians and safety and security to benefit Eritrea before Ethiopia.

They never was secretive to it! All of them be it Eritrean born blood or Tigrayan born blood from their jungle all the way until now: Seye, Gebru, Tsadkan, Meles, Abay, Seyoum, Sebhat, Tedros….all were and still in power continue to defend their original position.

Infact Asgede told us in his book. that at one time, Meles Zenawi was against sending Tigrayan fighters to Eritrea and was against EPLF (though, hard to understand why) when other Tigrayans went the contrary.

For your surprise brother Abraha Belay- it was openly given millions of Dollars and Airline, banks and dual citizen passports/sometime with no passport of Id card-to Eritreans that all the rights Ethiopians did not given.

This was openly carried. There was no secret. The chief designer for the Weyane Kililization apartheid admonition in Ethiopia was Meles. And that was supported and crazily loved by Tigrayans for implementing such Bantustan policy in Ethiopia. The Tigrayans were part and participants of the destruction and the pillage of Ethiopia with no secret attached to it. The subversion was and still is openly operating.

Ethiopians were removed by force from Eritrea their property taken away from them. Some killed, disappeared and raped. There was no secret. When Melese Zenawi openly support the ethnic cleansing by Eritreans again Ethiopians, the Tigray elite in power also went along with him. He did not do it in secret as you claimed foolishly and compared with Tesfaye Gebreabs secret spy mission.

It irritated me. Let me stop here.

Now to Bruk and Abraha Belay’s Mabo Jumbo accusation.

Mr Buruk: asked Abraha Belay- “…..ይህንን የሚያነሱ አንዳንድ ግለሰቦች ‘ኢትዮጵያዊያን ነን’ የሚሉ በተቃዋሚ ውስጥ ያሉ አክራራ right wing ምናልባት የቲ ፒ ኤል ኤፍ ተቀጣሪዎችም ሊሆኑ ይችላሉ፤ (እነሱ) ምንድ ነው የሚሉት “በዲያስፖራ ያለው የትግራይ ተወላጆች ወያኔን የሚቃወሙት በጣም ጥቂቶች ናቸው፤ አብዛኛው (የትግራይ) ሰው ግን ቲ ፒ ኤል ኤፍን ይድግፋል፤ እንዲሁም ትግራይ ውስጥ ዲቬሎፕመንት አለ፡ እያሉ ይህንን ፕሮፓጋንዳ ሊጠቀሙበት ይሞክራሉ። እኛም ውስጥ እንግዲህ ተቃዋሚዎች ነን ብለው ማንነታቸውን አናውቃቸውም፤ ነግር ግን ((ትግራይ ተጠቃሚ ነው የሚሉ) እንደዚያ የሚሉ ሰዎች/ተቃዋሚዎች አሉ። ለነሱ የሚሰጡት መልስ ምንድ ነው አቶ አብርሃ?”

የአብርሃ በላይ መልስ ከማየታችን በፊት፤ መጀመሪያ በፓልቶኩ አዘጋጅ “አቶ ብሩክ” ልጀምር (ግን ብዙ ልሄድበት አልፈልግም)። በብሩክ አመለካካት “የትግራይ ተወላጆች ወያኔን የሚቃወሙት በጣም ጥቂቶች ናቸው፤ወይንም ትግሬዎች በወያኔ ጊዜ ከተቀሩት ጎሳዎች ተጠቅመዋል።” የምንል ተቺዎች፤ “ማንነታችን የማይታወቅ፤ ቀኝ/አክራሪ፤የወያኔ ተቀጣሪዎች፤ፕሮፓጋንዲስቶች” ብሎናል።

ይህ ‘ደነዝ’፤ በቀኝ አክራሪ እና በወያኔነት አንዲሁም ማንነታችን በማይታወቅነት አድርጎ ሲስለን፤ አስገራሚው ነገር ፦ እኛ ትግሬዎች “ትኩስ ዕብድ” በከተማው ስናይ ሰውየው “ይህ አዲስ ነፋስ” ከየት መጣ የምንለው ዓይነት ስፓኒሾች “ሎኮ” የኒሉት ‘ዕብድ’ ሆኖ ነው ያገኘሁት።

ይህ ደብተራው ሊክ የተባለው ፓልቶክ “ኢካድ ፎረም/ካረንት አፈይር” የተባለው “የስሜተኞች፤ የሰካራሞች፤የሻዕቢያው የግንቦት 7 ደጋፊዎች እና የጎጠኞች ስብስብ” የተካው ይመስላል። አሁን የካረንት አፈይር እብዶች እና የአባ መላ እብዶች ወደ “ደብተራ ሊክ ፓል ቶክ” የኮበለሉ ይመስለኛል። ቁጥሩም የበረታበት ዋናው ምክንያት የኮብላዮቹ ዓይነት ይመስለኛል። የበርካታ ‘ጂሃዲሰት ኢስላም’ ክፍሎች ስትመለከቱ ክፍላቸው ከማንኛውም ፓል ቶክ ታዳሚ በቁጥር የበዛነው። በመርህ ከተመሮከዘ ይልቅ በርካታ ተጃጃሊ እና የቀወሰ ስሜተኛ ማስመጣት በጣም ስለሚቀል፤ ጎብኚው “በተከታታይ” የበረከተ ይሆናል።

አንድ ወዳጄ ሲነግረኝ ‘አዘጋጁ’ (ቡሩክ ማለቱ ነው) የሆነ ነገር እያነበበ “አበሻ” የተባለ ስም ትግራይ ውስጥ አንዳለ ካነበበ በሗላ “አያችሁ ‘አበሻ’ የሚል ስም ትግራይ ወንድሞቻችን ውስጥም ነበር ማለት ነው” ብሎ ሲል በሰውየው ትንሽ ጭንቅላት በሳቅ ነበር የተንከተከትኩት ብሎ ነግሮኛል።

አብርሃስ ምን መልስ ሰጠ? አብርሃ በላይ፤ ያመናቸው፤ያሞገሳቸው፤በድረገጹ ሲያሸበርቃቸውየነበሩት አርበኞቹ በየወቅቱ እየተንሸራተቱበት የተቸገረ ይመስላል። ስየ አብርሃ ሲንሸራተትበት አሁን ደግሞ፤ አብርሃ ደስታ የተባለ አዲስ አርበኛ አግኝቷል። ቋሚ አርበኛው ሆኖ የቆየው አስገደ ገብረስላሴ ብቻ ነው። አስገደ ደግሞ አርበኛ በመባሉ ተገቢ ነው። እኔም እስካሁን ድረስ በአድናቆት እና በጐ ዓይን የምቸረው ታጋይ ነው።በዛው ችግር የለብኝም።

እንዲህ ይላል አብርሃ በላይ

“ አዎ፣ አዎ፤ አየህ አብርሃ ደስታ አንድ ነገር ሲለጥፍ ተሽቀዳድመው ወድያውኑ ትችት የሚሰጡ እነኚህ የምትላቸው ሰዎች ናቸው።” ሲል በአብርሃ ደስታ ‘ቅዱስነትና ሙሉእነት’ የተማረከው አብርሃ በላይ፤- “አብርሃ ደስታን” መተቸት ማለት ቡሩክ እና አብርሃ አንደሚሉን “አክራሪ ቀኝ ሃይሎች፤ወያኔዎች፤ማንንታችን የማይታወቅ ግለሰዎች…” ነን ማለት ነው።

ይህ አዲስ እብደት አይደለም። በአብርሃ በላይ ብቻ አልተጀመረም። ስየ አብርሃ ሲመጣ፤ስየን በመተቸታችን፤ ስየ ጸረ ወያኔ ነው፤አዳኛችን ነው ተብሎ ሽር ጉድ ሲሉ በነበሩበት ወቅት፤ የሕግ ምሑር እና የሕግ አስተማሪው “አል ማርያም” በወቅቱ ‘ሲኒክስ’ ብሎናል። አብርሃ በላይ “የትግራይ ሕዝብ እንዲሸማቀቅ የሚያደርጉ፤ ጸረ አንድነት ሃይሎች ወዘተ…” ብሎናል። ስለ ነጋሶ ጊዳዳ ስለ ቡልቻ፤ ስለ ብርቱካን ስለ ኦ ኤል ኤፍ፤ ስለ ግንቦተ 7፤ ስለ ጃዋር…ስለ በየነ ጴጥሮስ” በተቸን ቁጥር ያልተባልነው ነገር አልነበረም። ሁሉም በየተራ ሲወድቁባቸው፤ ግን እነ …እነ…..እነ,፣ ይቅርታም አልጠየቁንም።

አብርሃ ደስታን አንዳትነኩት፤ወዮላችሁ እያሉ የሚሰድቡን በርከት በርከት ብለዋል። የአብርሃ በላይ አዲሱ አርበኛ ‘አብርሃ ደስታም’ እኮ “ትግሬ ተጠቅሟል፡ የሚሉ “የትግራይ ሕዝብ ጠላቶች ናቸው፤ደርጎች ናቸው ብሎናል”። ትግራይ እሱ ብቻ ወይንም እነሱ ብቻ የተወለዱባት መሬት መስሎ የሚታያቸው “ብዙ ከብቶች” አሉ። በነዚህ ትንንሽ “ጎሰኞች” ጭንቅላት የትግራይን ሕዝብ ነባራዊው ሃቅ ስለተናገርን፤ “ትግሬነታችን” የመስጠት ወይንም የመንጠቅ ሥልጣን ያላቸው መስለው እየታያቸው ነው። እነ አብርሃ በላይ እና አብርሃ ደስታ እኮ “ፋሺስት ወያነ ትግራይ” የሚለንን እኮ ነው እየደገሙት ያሉት። ስለ ትግሬዎች ፖለቲካ የሚተች ሁሉ፤ “የትግሬ ጠላት” “ወይንም “ትግሬዎች አይደሉም፤ ሽዋውያን ተጋሩ ናቸው” ብሎ ድሮ በወጣትነታቸው ወያኔ ያስተማራቸውን ዝባዝንኬ ነው እየደገሙት ያሉት። እንዲህ ብሎ ለሚወላፈጥ ግለሰብ መልስ እና ትችት መተቸት፤ በአብርሃ በላይ እና ባንዳንድ ትንሽ ጭንቅላቶች “አክራሪዎች/ቀኞች እና የትግራይ ሕዝብ ጠላቶች ነን” ተብለናል።

አስገራሚወ ነገር ለበርካታ አመታት እኛ ጥቂት ሰዎች ወያኔን ስንቃወም የኖርነው ሰዎች፤ ወያኔን ሲያገለግሉበት ከነበሩበት ኢትዮጵያ ወደ እዚህ መጥተው እኛን ‘ፀረ ሕዝብ ፤አክራሪዎች ብሎው ሲሰይሙን ትግራይ ውስጥ የኖሩ ትግርኛ ተናጋሪ አማራዎች ለዛ ባለው ምላሳቸው “ወይ ትገርምኒ” (ትግርሚኛለሽ) የሚሉት ነገር ነው።

አብርሃ ደስታ ወያኔን መቃወሙ የሚጠበቅ እና የሚያስመሰግነው ነው። ነገር ግን አማራን ከተወለደበት አገሩ ይባረር የሚለትን አን ጃዋር መሐመድን እና የሻዕቢያው ተስፋዬ ገብረአብን “ይመቹኛል፤ አትንኳቸው፤ይቀጡሉበት” እያለ ሲወላፈጥብን እና በአማራ ሕዝብ ሕይወት አንደ የፖለቲካ መጫወቻ ካርድ ሲመለከተው መተቸታችንን በአብርሃ በላይ እና በስሜት የሚወነጨፉ መሰል ጋላቢዎች ስንዘለፍ “ከትገርምኒ” በላይ ነው። ዛሬ አስተዳዳሪው ትግሬ ሳይሆን ሌላ ተመሳሰሳይ ዱርየ ሥልጣኑን ይዞ ቢሆን ኖሮ እና ትግሬ ከኦሮሞ፤ከጋምቤላ…እየተገደለም ግማሹም ከያለበት እየተጎተተ ወደ ትግሬ ሲባረር ብያይ፤ ወይንም በየዳር ትምህርት ቤቱ በየደረንዳው ተጥሎ የትግሬ ህፃናት ከእናታቸው ጉያ ተለጥፈው በብርድ እየተሰቃዩ ስቅስቅ ብለው ሲያለቅሱ በቲቪ፤ በሬዲዮ በቃለ መጠይቅ (አሁን እንደ አማራዎቹ እየተደረገ እንዳለው) ቢያዳምጥ ኖሮ፤ ለጃዋር እና ለተስፋየ ገብረአብ የሰጠውን ማአዛዊ ፍቅር ያሳይ ነበር? አይመስለኝም; ስሜቱ እጅግ ይለዋወጥ ነበር። አይደለም እነ ጃዋርን እና እነ ተስፋዬን አትንኩብኛ እና የአማራን መጠቃት በጽሑፍ ከማውገዝ ይቅርና ፤ ትግሬዎች ቢጠቁ ኖሮ ‘ ምድረ ትግሬ’ ጸጉሩን አቁሞ ፤ ዓይኑን ደም አልብሶ ነበር ዓለምን በሞላ ‘መሬት ቀወጢ” ያደርግ የነበረው።

አብርሃ በላይ የሚገርመው ደግሞ “እባካችሁ አስተምሯቸው” ብሎ ደግሞ ለደብተራ ፓልቶክ ታዳሚዎች ይማጠናል። እኛኑን ማለት ነው። “ትግሬ ስልጣን ላይ አይደለም፤ አብዛኛው ትግሬ የወያኔ ተጠቃሚ እና ደጋፊ ነው” ማለታችንን እንድናቆም የፓልቶከክ ፕሮፌሰር “አዋቂዎች” የሆኑት ማንነታችን የማይታወቅ የትግሬዎች የጎሳ ፖለቲካ የምንተች እኛኑን ሊያስተምሩን ማለት ነው። እሱ እራሱ ሊያስተምረን ያልቻለውን እነ ብሩክ ሊያስተምሩን ማለት ነው። “ወይ ትገርምኒ”!

ትግሬው የወያኔ ደጋፊ ካልሆነ ተቃዋሚም አይደለም። መረጃው ከአብርሃ በላይ የቅርብ ወዳጁ ምን አንዳለን እነሆ ላስቀምጥ እና ልደምድም።

መኮንን ዘለለው ይባላል። የታንድ አመራር አባል ነው። ወያኔን ይቃወማል። ስለ ትግሬዎች የሚነግርን አንድ ነገር አለ። ይህ የምጠቅሰው ጥቅስ እኔ ለመኮንን ዘለለው ባንድ አጋጣሚ የሰጠሁት መልስ የተቀነጨበ ነው።

እንዲህ ይላል፤- ልጥቀስ፡-

አዎ ትግሬዎች በጣም ጥቂት ካልሆኑ በቀር፤ ወደ ትግሉ አልተቀላቀሉም። ይኼ ደግሞ ፓልቶክ ሩም ሆነህ መቀላቀላቸው ብትመጻደቅና ትግሬዎች ተቀላቅለው እየታገሉ፤ ጌታቸው ረዳ ግን ትግሬዎች ወደ ትግሉ አልገቡም፤ አልታገሉም፤ ይለናል፤ ብለህ ብታወግዘኝም። ከኔ ይልቅ አንተ በራዲዩ ቃለ መጠይቅ ተጠይቀህ ምን እንዳልክ ባጭሩ ልግለጽልህ እና አውነተኛው እና ሃሰተኛው ማን እንደ ሆነ ለአንባቢ እንዲመች ቃልህ ይኼው፡

የሚከተለው ‘መኮነን ዘለለው’ ከአዲስ ደምፅ ጋር ያደረገው ምልልስ ነው።

ጥያቄ፦ አበሁኑ ሰዓት የትግራይ ተወላጆች በትግሉ ጎራ ለመቀላቀል ፍላጎት እንደሌላቸው በግልጽ የምናየው ጉዳይ ነው፡ ለምን እንዲህ ሆነ?

ከዚህ ቀጥሎ የመኮንን መልስ ግን ቃል በቃሉ ምንም ሳይታረም አቀርባለሁ። በቅንፍ ሲሆን ግን አማርኛውን ለማቃንት የተጨመረ ነው። መኮንን ዘለለው፦ የትግራይ ሕዝብ 90% ወይንም 100% (90 ከመቶ ወይንም 100 በመቶ) የመንግሥት ተቃዋሚ ነው። ሚስቱ የከዳቺው ሰው(ባል) ለመታገል ዝግጁ የሆነ አይመስለኝም።

የትግራይ ሕዝብ ባሳደጋቸው በልጆቹ የተከዳ ሕዝብ ነው። አንድ ሰው የሚያምናት ሚስቱ በሚስቱ የተከዳ ሌላ ሚስት ለማግባት የሚሮጥ አይመስለኝም። ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልገዋል። የትግራይ ሕዝብም እንደዛው ነው።

ትናንትና ልጆቼ ብሎ ወደ ትግሉ የላከ ልጆቹ ራሳቸው የከዱት ሕዝብ ነው እና አሁን በቀጥታ ወደ ትግሉ ለመግባት በማሰብ ላይ ነው። አርቆ የሚያስብ እውነተኛ የሚታመን የትግል ድርጅት እስካሁን አልተገኘም። እከሌ አለ የምትልም አይመስለኝም። አሁን

የትግራይ ሕዝብ በጠቅላላ አሁን ኢትዮጵያዊ እምነት ያለው የትግራይ ሕዝብ እየጠፋ ነው።

አሁን ያለው የትግራይ ሕዝብ ማን አለ እስቲ ከኢሕአዴግ ሃይል የተሻለ የሚል ነው። የተቆረቆረ የትግራይ ሕዝብ የምንሰማው እና ከዚህ መንግሥት የተለየ ጠባይ የተለየ አቀራረብ እንዲኖረን ያስፈልጋል።….”

በማለት የትግራይ ሕዝብ የወያኔ ደጋፊ እንደሆነ/እንደነበረ በቃልህ ነግረኸናል። የትግራይ ሕዝብ ከወያኔ የተሻለ ተቃዋሚ የለም እንደሚል ነግረኸናል። እንደገና ወያኔዎች ስለከዱት ወደ ትግሉ ጎራ መግባት አልፈለገም። ብለሃል። ስለዚህ ጌታቸው ረዳ ምን ባጠፋሁ ነው፤ “ትግሬዎች አይታገሉም ይላል፡ ብለህ በኔ ላይ ውርጅብኝ የወረድከው? ይኼ አቋምህም እኮ ከነ ታማኝ በየነ ጋር በአዲስ ደምጽ ራዲዮ ተከራክረሃል/ደግመኸዋል። ታማኝ ምን ብሎ እንደመለሰልህ/እንደጠየቀህ አንተ ምን ብለህ እንደተናገርክ ታስተውሰው ይሆናል።

እኔ ያለ መረጃ ሰውን አልነካም ፤ ሲነኩኝ ነው እኔም ሃቁን ለማውጣት ሁሌም ራሴን ለመከላከል የምጋፈጠው። ከማንኛችሁም ጋር የምጋፈጠው ስለ አገር እንጂ በግል ተነሳስቼ የማገኘው ነገር ወይንም ጥቅም እንደሌለ ይታወቅልኝ። ማንም ሊወደኝ ወይንም ሊጠላኝ ይችላል; ሁለቱም የየሰው መብት ነው፤ አከብረለታለሁ። አንድ መታወቅ ያለበት ግን እዚህ ትግል ስገባ “ሰውን ለማስደሰት/ለማስቀየም/ለመወደድ/ ለመጠላት/ለመሾም/ዝና ለማትረፍ/ለመዋረድ ለማዋረድ/ በሚል አይደልም። የሚሰድቡኝ ካሉ ይበልጥኑ እራሳቸው ተመልሰው ማየት ይኖርባቸዋል። እንደ ማልምራቸው የምታውቁት ነው። አገርን መዝለፍ ያልከበዳቸው እኔን አንድ ግለሰብ መስደብ ይከብዳቸዋል የሚል ሕልም የለኝም። ስለዚህ ክቡራን ወንድሞቼ ምስኪኑ ጌታቸው ረዳን በየፓል ቶኩ ስሜን ባታነሱ እና የማቀርበውን ትችት ብትጋፈጡ ይመረጣል። አቶ መኮንን ለትግልህ እና ለዕድሜህ አክብሮት እሰጣለሁ።”

ስል ባንድ አጋጣሚ መልስ ሰጥቸው ነበር። ይህ ያመጣሁት አብርሃ በላይም ሆኑ መሰሎቹ ማስተዋል ያለባቸው ነገር፤ መኮንን ዘለለው የሚለንን በቅጡ እንዲመረምሩት እና እኛን መዝለፍ አንዲያቆሙ ነው። ከዚህ የምንማረው አንግዲህ የትግራይ ሕዝብ አቋም ከነመኮነን ዘለለው ወዲያ የሚያውቅ ያለ አይመስለኝም። መኮንን የነገረን ደግሞ ሃቁ ከላይ ጠቅሻለሁ።

ስለዚህ አብረሃ በላይም ሆነ ሌሎቻችሁ ከላይ ያቀረብኩትን ነጥብ መምታት ከቻላችሁ ‘እሰየው” ይኸው ሜዳው እና ፈረሱ። እኛን ያለ ማስረጃ መከራከር ግን ወያኔዎችን ለዘመናት የታገልነው ሰዎች አክራሪዎች/ቀኝ/ወያኔዎች/የማይታወቁ ሰዎች ወዘተ… እያላችሁ መሳደቡን ትንሽ እፈሩበት። ዓየሩን ቀድመን የተነፈስነው እያለን? ኋላ የመጣ ዓይን አወጣ! አመሰግናለሁ።

ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ብሎግ አዘጋጅ) Getachew Reda (Editor Ethiopian Semay)getachre@aol.com  

የጃርት ጉባኤ ርደት (ሥርጉተ ሥላሴ ሲዊዘርላንድ -ዙሪክ)

$
0
0

ባድማ በጃርት ተሰቅዛ

በአረማሞ አራሙቻ ናውዛ

እህህን ሰንቃ ደንዝዛ

ሰቀቀን ታጥቃ አርግዛ።

ሬት ጨጎጎት ተደልዛ

መቀነት በእሾኽ ተገንዛ፣

ቁም ስቅሏን አዬች

ይህው በልዛ።

`ጃርተ ምርት እሾህ

ፍጥረተ ነገሯ ውጋት

በበቀል – ተዋቅራ

በደም – ተቋድሳ

በደጋን ታምሳ – ተደቁሳ፤

እሾህ አዘራች መልሳ፤

የጃርት ገላ መላልሳ።

ህልመ ራዕዩ ምልግልግ

የላንቁሶ ውሃ ዝልግል

ጃርተ – ልብ፤ የእሾህ ልግ

የአሜክላ የቋሳ ድግዳግ።

ጃርትስ አሰኛት የበቀል ብቅል

ቋቱ ’ማያውቅ ግል

የጃርት ህሊና የውጋት ግልል፣

ሰባራ ገል።

እሾህስ አልቦ የለም ጃርት

ከዘረ እሾህ የለም ምርት

የጠቀራ ናስ ሃሞት

ዙሪያ ገባው ማት፤

… ህልፍት የሐገር ቅብረት።

አንተ አለህና በቤትህ

ትሰማለህም ታያለህም

የጃርትን ትዕቢት፤ … የቀን ጥሰት

የበቀል አምላክ አትለፋት፤

የህዝብን ዕንባ ህማማት፤

እ!-እ!-እ!-እ!እ!-እ!-

እም – እም – አም እ——-ም!

 

ውስጥ

 

ይህን ግጥም ለመጀመሪያ ጊዜ መድረክ ላይ ያቀርብኩት የመጀመሪያዋ ሐገራዊ ፓርቲ ሊ/መንበር ክብርት ዳኛ ብርቱካን ሜዴቅሳ የፓርቲያዋን የአንድነትን ዓላማና ተግባር ለማስተዋወቅ፤ እንዲሁም ደጋፊ አካላትን ለማዋቀር እ.አ.አ በ2008 በታህሳስ ወር አውሮፓ በተዘዋወረችበት ወቅት ሲዊዝ ጄኔባ  መጥታ በነበረችበት ጊዜ ነበር። ከመክፈቻ ንግግሬ በኋላ ግጥሙን አቅርቤ ስጨርስ እንዲህ አለች „አንቺ ምን አለብሽ?! እንዲህ የልብሽን በነፃነት ታቀርቢያለሽ። እኛ የግጥም ምሽት አዘጋጅተን ከቢሮችን ውስጥ በታጣቂዎች ተከበብን“ በማለት ተክዛ ቆዬችና አይኗን ወደ እኔ ላከችው።

eth cryአዬሩ ፈቅዶ ሁለታችንም አገናኘን። በመንፈስ ተቀራረብን – ተዋኽድን። አስተውላም አዬችኝ በውስጧ – እኔም ምላሹን ደረብኳት። ህልሜ ተሳክቶ ሴት አቅሟን ብቃቷን እንዳዛ በወሳኝ የኃላፊነት ቦታ በእርግጠኝነት ስታቀርብ ከማዬት በላይ ሐሴት አልነበረም። ተስፋውንም ቀጠልኩበት። ቃሌን ሳላጥፍ ከተግባር አርበኞቿ፤ ከሲዊዝ የአንድነት ድጋፍ ሰጪ አካሎቿ ጋር ጥሩ የሰመረ የሰላም ጊዜ አሳለፍን። እንዲሁም በአለም ዙሪያ ካሉ ተቆርቋሪዎቿ ጋርም የሚያስመካ የፍቅር አንድነት ገነባንበት። አቅለ ቢሱ ወያኔም ስትመለስ እግር ብረት ለእሷና ለልጇ ለሀልዬ አዘጋጅቶ ቢጠባቅታም ደጋፊዎቿ ግን በያሉበት ታጥቀውና ተግተው ታገሉ። ከአውሮፓ ወደ ቃሊት። እጅግ አስደንጋጭና መራራም ነበር። ዛሬ ደግሞ ለሴት ተቆርቋሪ ሆኖ ሙጃው ወያኔ አለሁኝ ሲል አዳመጥን።

እኔ በግሌ ከጃርት የእሾህ ፈል እንጂ ሌላ እምጠብቀው የለም። ጠንከር ያሉ ትችቶችን ላጥ አድርጎ ማስመሰሉን አቀለጠበት – አይፍር መንፈሱን በአሻቦ ያወራረደ – ግልብ። እንደዚህ ላጥ እያደረገ ቀሰማውን እንደሚያስነካው ስለምን የተባበሩት መንግስታት ድንጋጌዎች አክብሮ በሰቧዕዊ መብት ላይ የሚደልቀውን ጭፈራ አይገታም? ወኔ ካለው በሺህ የሚቆጠሩ ሴት እስረኞች ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፍታ። ከዚህ ከለበጣ ኮሜዲ ተግባሩ በፊት። ሲያንጎላች ይከርምና እንዲህ ይባንናል – የጉም ሽንት። ለቅብ እንዳረገደ እንዳረገረገ 23 ዓመት —– ነጎደ።

የኔዎቹ በሉ ተመራርቅን አንለያይ። የተመቼ ጊዜ እንሆ ተመኘሁላችሁ። ፍቅርና ናፍቆት በገፍም ተላከ ለእናንተ ——– — ለክብረቶቼ።

ማሳሰቢያ — 1.   ግጥሙ – ግንቦት 20 ቀን 2000 ዓ.ም ክላይነአንደልፊንገን – ሲዊዘርላንድ ተጻፈ። ከመጀመሪያው መጸሐፌ „ተስፋ“ ላይ ከገጽ 49 እስከ 50 ይገኛል።

2.  ይህቺ ምልክት ለንባብ እንዲያመች አንድ ፊደል መዋጡን ታመልካታለች – ከትህትና ጋር።

ለቅሶ የሚያበቃበት ቀን ናፈቀኝ!

እግዚአብሄር ህዝባችንና ልዕልት ኢትዮጵያን ይጠበቅ። አሜን!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

ሰበር ዜና –የአዲስ አበባ መስተዳድር የእውቅና ደብዳቤ ጻፈ ፓርቲው አልተስማማም::

$
0
0


አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ለመጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም ሊያደርገው ለነበረው ሰላማዊ ሰልፍ የመስተዳድሩ የሰላማዊ ሰልፍና ማሳወቂያ ክፍል ዘግይቶ በጻፈው ደብዳቤ የሰልፉ ቀን በሌላ ፕሮግራም መያዙን በመጥቀስ የቀን ለውጥ እንዲደረግ መጠየቁ አይዘነጋም፡፡
ፓርቲው የቀረበውን አስተያየት በመቀበል ሰልፉ ለሚያዚያ 5 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲደረግ መወሰኑን በመግለጽ ለመስተዳድሩ አሳውቋል፡፡ሆኖም መስተዳድሩ ዕለቱ በታላቁ ሩጫ መያዙን በመጥቀስ ለፖሊስ ጥበቃ ለመስጠት የሚያስቸግረው በመሆኑ ሰልፉ ለሚያዚያ 4 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲደረግ የእውቅና ደብዳቤ ጽፏል፡፡ፓርቲው በመስተዳድሩ የተሰጠውን እውቅና አለመቀበሉን ለማሳወቅ ከፍተኛ አመራሮቹን ወደ ከንቲባው ጽ/ቤት ልኳል፡፡
በአሁኑ ሰዓትም አመራሮቹና የመስተዳድሩ ሰዎች በጉዳዩ ዙሪያ እየተነጋገሩ ነው፡

Andinet AA Application

 

ኦሮሞ ነኝ የሚለው ብዙው ሕዝብ በታላቁ ኢትዮጵያዊ ሚንሊክ ላይ ያለው ጥላቻ ከምን የመጣ ነው?

$
0
0

የታላቋ ቀን ልጅ
ሚያዝያ 1 2006 ዓ.ም.

minilik

ታላቁ ኢትዮጵያዊ ሚንሊክ

እጅግ ክፉና ማንነትን ከሚያዋርዱ ነገሮች አንዱ አእምሮን ከእውነትና ማስተዋል አስርቦ መነሻው ምን እንደሆነ ብዙዎች በማያውቁት ስሜተኝነት መነዳት ነው፡፡ ይን የሰው ልጆችን በስሜተኝነት የመጥለፍ አጋጣሚን ለመፍጠርና በተፈጠረውም አጋጣሚ ራሳቸውን አግዝፈው የሚኖሩ ግን በተፈጥሮ ብስለታቸው የወረዱ ሌሎችንም በእነሱ ደረጃ ከእነሱም ባነሰ ሊያዋርዱ ሌሊት ከቀን እንቅልፉ የሌላቸው ከዚያም በላይ በዕርኩሳን መናፍስት የሚታገዙ ሰብዐዊ ፍጡሮች በዙሪያችን እንደሚያንዣብቡ ብዙዎቻችን አንረዳም፡፡ እንደነዚህ ያሉ ሰዎች አእምሮአቸው በጎ እንዳያስብ የነጠፈና  በምትኩ ክፋትን ከቀን ወደቀን በማሳደግ ራሱን ሰይጣንን የሚተካ ባሕሪን ያዳበሩ ናቸው፡፡  በዚህ አደገኛን በመረቀዘ አእምሮአቸው ሌሎችን የመርዛሉ ያጠፋሉ፡፡ እነዚህ ሰው የሚመስሉ ግን በአካል የሚንቀሳቀሱ ሰይጣኖች ከሚበዙባቸው ቦታዎች ደግሞ ሕዝብ ትላልቅና የተከበሩ ብሎ በሚያስብባቸው ከፍተኛ አመኔታ በሚሰጣቸው ነው፡፡ ከነዚህም ውስጥ የፖለቲካ የሥልጣን መዋቅሮችና የሐይማኖት ተቋሞች ቀዳሚውን ቦታ ይይዛሉ፡፡

ከላይ የተጠቀሱት ሁለቱ መዋቅሮች ባሉ መሪዎች ላይ ሰዎች ከፍተኛ አመኔታን ይሰጣሉ፡፡ ግን ብዙ ጊዜ ለአመኔታቸው አጸፋው መልካም ነገር ላይሆን ይችላል፡፡ ብዙም ጊዜ ወድቀትና ወርደት ይሆናል፡፡ ሁለቱም መዋቅሮች እጅግ የበሰለ አእምሮን፣ ቅንነትን፣ የሕዝብ እንደራሴ መሆንን የሚጠይቁ ቢሆም በብዙ የታሪክ ገጠመኞች ግን ተቃራኒው ሲሆን ይስተዋላል፡፡ በአሁን ዘመን ደግሞ ከመቼውም የከፋ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ እነዚህ ከላይ የተጣለውን ሰይጣን የሚወክሉ ሰብዓዊ ፍጥረቶች በቅንነትና በበሰለ አእምሮ ለሕዝብና ለአገር ክብር የነበሩ ሰዎች ታሪካቸው እንዳይታወቅ፣ ከታወቀም ራሳቸው በፈጠሩት ሌላ ታሪክ የእነዚህን ባለታሪኮች ታሪክ በማጉደፍና የቀደመ ታሪክን የማያውቅ ሌላ እነሱን የመሰለ ትውልድ ተክቶ የታላላቅ ባለራዕዮችን ታሪክ ጨርሶ እንዲጠፋ በማድረግ የእነሱን ኑሮ ማደላደል አንዱ መገለጫቸው ነው፡፡

እኔ የምናገረው ከስሜተኝነት የተነሳ እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ ግን የተረዳሁትን ያህል እናገራለሁ፡፡ ባለማወቅ ግን ልሳሳት እችላለሁ እኔ የተረዳሁት ስህተት ሊሆን ስለሚችል፡፡ የሚያርመኝ ካለም እቀበላለሁ፡፡ ደግሜ እናገራለሁ ከሥሜት የተነሳ አላወራሁም፡፡

በእኔ ግንዛቤና መረዳት በአለፉት አምስተ መቶና ምንአልባትም ከዚያም በላይ እንደ ኢትዮጵያዊው መሪ ሚንሊክ ያለ መሪ በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካም ብቻ ሳይየሆን በአለም ላይ ነበረ የሚለኝን የታሪክ ምሁር ትንተና እሻለሁ፡፡ እኔ በአለፉት አምስት መቶ ከዚያም በላይ በሚሆን ዘመን እንደ ኢትዮጵያዊው ሚንሊክ ያለ ታላቅ መሪ እንዳልነበረ አስባለሁ፡፡ በእኛው ዘነድ ስለሚንሊክ ያለን ግንዛቤ ወይም ከላይ በጠቀስኳቸው የወረዱ አእምሮዎች የጎደፈ ወይም በእጅ የያዙት ወርቅ አይነት ብዙም ትኩረት ያልሰጠነው ይመስለኛል፡፡

ዛሬ በአብዛኞቻችን ዘንድ የሚንሊክ ታሪክ እንኳንስ የማንነታችን መገለጫ አድርገን የምንኮራበት በአንደበታችንም ለመናገር የሚቀፈን ሆኗል፡፡ ብዙዎቻችንም በመርዝ በተለወሰ ሌላ ታሪክ አእምሮአችን የታላቁን ሰው ታሪክ የሚያጎድፍ፡፡ በተለይም  በኢትርዮጵያ ትልቅ ቁጥር አለው ተብሎ በሚታመንለት ኦሮሞ እየተባለ በሚጠራው አብዛኛው ሕዝብ ዘንድ ዛሬ የሚንሊክ ጉዳይ ሲነሳ ያስበረግገዋል፤ እጅግ ያስቆጣዋል፤ ሥሙን አታንሱብኝ ይህን ሥም ከታሪክ ደምስሱት ጩኸት ያሰማል፡፡ ምክነያት ተብሎ ሲጠየቅ በዋነኝነት ብዙ ጊዜ የሚነሱት በሐረር የጨለንቆ ጦርነትና በአርሲ በሚንሊክ ዘመቻ ተፈጸሟል ተብሎ በዘበናውያን ታሪክ አዋቂዎች ነን ባሉ የተሰበከው የጡትና እጅ መቁረጥ (ሀርካ ሙራ ሐርማ ሙራ) ግፍ ነው፡፡

ሚንሊክን ታላቅ ከሚያሰኛቸው ታሪክ አንዱ ዛሬ ኢትዮጵያ ብለን የምንጠራትን አገር አንድ በማድረጋቸው ነው፡፡ ኢትዮጵያን አንድ ያደረጉበት ሂደት ደግሞ አልጋ በአልጋ የነበረ ሳይሆን ከብዙ በየስፍራው በነበሩ መሳፍንቶች ጋር ተዋግተው ነው፡፡ በወቅቱ እንደአሁን ዘመን ዲፕሎማሳዊ ሂደት ብዙም የሚያስኬድ አልነበረም፡፡ ሆኖም ሚንሊክ እርግጥም ከዘመኑ በፊት የተፈጠሩ ታላቅ ሰው ስለነበሩ ዲፕሎማሳዊው ሂደት ሁል ጊዜም ቅድሚያ የሰጡት ነበር፡፡ አንድም መስፍን (የአካባቢ መሪ) የሚንሊክን ታላቅ ራዕይ ሳይቃወም ጦርነት የከፈቱበት የለም፡፡ በወቅቱ ግን በነበረው የመሳፍንቶች ኋላ ቀር አስተሳሰብ ከሚንሊክ የቀደመ አስተሳሰብ ጋር የሚጣጣም ባለመሆኑ የሚንሊክን አገርን የመገንባት ሂደት የሚተባበር አልነበረም፡፡ የእነዚያ ኋላ ቀር የአካባቢ መሪ ተብዬዎች ሕልም ለራሳቸው ከርስ የሚሞላ ሕዝብን ከመግዛት ያለፈ የዕድገትና ብልፅግና ሕልም ከቶውንም አልነበራቸውም፡፡ ይህ ደግሞ የሕዝብና የአገር ውርደትና ኋላ ቀርነት እንደ እሳት ለአንገበገበው ሚንሊክ እንቅፋት ነበር፡፡ በመሆኑም ሚንሊክ የወደደውን በውድ ያልወደደውን በግድ ማሳመን ይጠበቅባቸው ነበር፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ከብዙ ኋላ ቀር አስተሳሰብ ካላቸው የአካባባ መሳፍንት ጋር ጦርነት ገጥመዋል፡፡ በጦርነቶቹ ሁሉ የባለራዕዩ የበላይነት የግድ ቢሆንም ጦርነት ጦርነት ነውና ብዙ ጥፋቶች ጠፍተዋል፡፡ ከሁሉም በላይ ግን የሰዎች ልጆች አልቀዋል፣ ተሰቃይተዋል፡፡ ይህ ሁሉ ግን የሚንሊክ ፍላጎት ሳይሆን የመሳፍነቶቹ ምርጫ ነበር፡፡

በሀረር ጨለንቆና አርሲ የተከሰቱ ጦርነቶች ሚንሊክ አገርን ለመገንባት ካደረጓቸው ሁለቱ ናቸው፡፡ የጨለንቆው ጦርነት በአስከፊነቱ ብዙ ሕዝብ ያለቀበት ቢሆንም በጦርነት ከሚከሰቱ የተለመዱ ጥፋቶች ሌላ ለየት ያለ የታሪክ ጠባሳ ያቆየ አልመሰለኝም፡፡ የአርሲው ጦርነት ግን እስከዛሬም ድረስ እንዲረሳ አጋጣሚን ለመጠቀም በሚፈልጉ መርዘኞች እንደ መሣሪያነት እያገለገለ ነው፡፡

ሀርካ ሙራ ሐርማ ሙራ! በአማርኛ እጅ መቁረጥ ጡት መቁረጥ ማለት ነው፡፡ ይህ አሳቃቂ ግፍ በአርሲው የሚንሊክ ዘመቻ ተከስቷል እየተባለ ዛሬ ባለው ትውልድ ልዩ ስፍራ የተሰጠው አልፎም ሐውልት የቆመለት ጉዳይ ሆኗል፡፡ እኔ እንዲህ ያሉ ግፎች በዚያ ዘመን በነበሩ ጦርነቶች ሊከሰቱ ከሚችሉ አሳቃቂ ክስተቶች አንዱ ሊሆኑ እንደሚችሉ አምናለሁ፡፡ ሆኖም በአርሲ ተከሰተ የተባለው እንዲህ ያለ ግፍ የታላቁ ሰው ሚንሊክ ትዕዛዝና ይሁንታ አለበት ብዬ አላምንም፡፡ በብዙ ጦርነቶች እንደሚከሰተው፣ ይልቁንም በዚያ የጠበቀ የጦርነት የመምራት አቅምና ቅንጅት በሌለበት ዘመን ከተዋጊዎች አንዱ ወይም ከዚያም በላይ እንዲህ ያለውን ጥፋት ፈፅመውት ይሆናል፡፡ ሚንሊክ ግን እንዲህ ያደረጉትን ወታደሮች ማንነት ቢያውቁ የሚሸልሟቸው እንዳልሆኑ አምናለሁ፡፡ ይልቁንም በሞት ሳይቀር ሊቀጧቸው እንደሚችሉ አምናለሁ፡፡ ይህ የሚንሊክ እውነተኛው ልብ ነው! ሚንሊክ እውነተኛ ጀግና የሚባል ባሕሪ ያላቸው ናቸው፡፡ ጀግና ደግሞ ጨካኝ አይደለም! ጀግና ጠላቶቹ የማይቋቋሙት እንጂ! እነኳንስ በሴቶችና አቅም በሌላቸው ላይ ሊያጠፋቸው የመጣን ጠላት እንኳን ከመግደል ይልቅ ከእነነፍሱ ይዘው ምህረትን ሊያደርጉለት የሚፈልጉ ናቸው፡፡ ጠላታቸውን እንኳን ገድለው በሬሳው ላይ የሚጨፍሩ አይደሉም፡፡ ይልቁንም አስቸጋሪና የተቋቋማቸው ጠላታቸውን ሲጥሉት ለአስከሬኑ ሳይቀር ክብርን የሚሰጡ ናቸው፡፡ እንዲህ ያለው ተቃራኒ ጠላት የሆነ ግን ጀግና አስከሬን ለውሻና ለአውሬ የሚሰጡ ሳይሆን በክብር የሚቀብሩ ውጊያውን የአላማ እንጂ የተፈጥሮ ጠላትነት እንዳልሆነ የሚያስቡ ናቸው፡፡ ሰውን በሰበዐዊነቱ የሚያከብሩ ልዩ አመለካከት ያላቸው ናቸው፡፡ ይህ የእውነተኞቹ ጀግኖች ልዩ መገለጫ ነው፡፡ ሚንሊክ ይህ ባሕሪ ልዩ መገለጫቸው ከሆኑ አንዱ ነበሩ! በነዚህ መስፈርቶች መሠረት ግን ብዙዎች በኢትዮጵያ ጀግኖች እየተባሉ የተወደሱትን ማንነት ቴዎድሮስን ጨምሮ እጠራጠራለሁ፡፡ ይልቁንስ በቅርብ ታሪክ የምናውቀው ሕወሐት አባል የነበረው ኃያሎም አረአያ እነዚህ የጀግኖች ልዩ መገለጫ ያልኳቸው ባህሪያት እንደነበሩት ብዙ የሰማቸው ገድሎቹ ይናገራሉ፡፡

እንግዲህ በስሜትና በጥላቻ በመረቀዙ አእምሮዎች ሳይሆን እውነትን ለመጋፈጥ በሚደፍሩ አእምሮዎች እኔ የተረዳሁትን የሚንሊክን ማንነት አይደለም የሚል ካለ ለማደመጥ እወዳለሁ፡፡ ሚንሊክ ሩሩህና ይቅር ባይነታቸው ባደረቸው ጦርነቶች ሁሉ በደረሱ እልቂቶችና ጥፋቶች እጅግ ይጸጸቱ ነበር፡፡ ችግሩ አማራጭ ብቻ በማጣታቸው ጦርነቱ ግድ ሆኖማቸው እንጂ፡፡ በደረሰው ጥፋት ካዘኑባቸው ጦርነቶች አንዱ ደግሞ የአርሲው ጦርነት ነው፡፡ በጦርነቱ አሸንፈው አገሩን ከተቆጣጠሩት በኋላም ወታደሮቻቸውን ሕዝቡ ባለማወቁ ምክነያት የደረሰበትን እልቂት አሳዝኗቸው ወታደሮቻቸውን አሸንፌያለሁ በሚል በሕዝቡ ላይ ሌላ በደል እነዳያደርጉበት አዋጅ አውጥተው ሁሉ ነበር፡፡ ለወታደሮቻቸውም የአርሲን ሕዝብ ሲገልጹት ወንድምህ የአርሲ ሕዝብ እያሉ ነበር እንጂ እንደ ጠላት አልነበረም፡፡ ይህን እውነታ የታሪክ አዋቂ ነን የሚሉት ለምን ለሕዝብ ለማሳወቅ አልፈለጉም፡፡ ይልቁንስ የሚንልክ ትዛዛዊ ግፍ ለመሆኑ አጠራጣሪ ስለሆነው ሀርካሙራና ሀርማ ሙራ ማግዘፍን ለምን ፈለጉ፡፡ ሌላው የሚንሊክ ማንነት የተገለጸበት ጦርነት የወላይታው ከንጉስ ጦና ጋር የነበራቸው ጦርነት ነው፡፡ ንጉስ ጦናን አሸንፈው በእጃቸው ካገቡና አላማቸውን ከአሳመኗቸው በኋላ ንግሰናቸውን አጽድቀው እንደሾሟቸው ይነገራል፡፡ ከዚያም በላይ ጦና በጦርነቱ በመቁሰላቸው ምክነያት ሌላውን ሰው ባለማመን ሚንሊክ ራሳቸው እየተከታተሉ እንዲታከሙ ማድረጋቸው ይነገራል፡፡ ሌሎችም አያሌ የሚንሊክን ሕይወት የሚናገሩ መዛግብቶች ሩሩሕና የጅግና ሰው ልዩ መገለጫ የሆኑትን ባሕሪያቸውን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ሚንሊክ ጋር በቀል የለም ጭጋኔም የለም የአላማ ጽኑነትና ታላቅነት እንጂ፡፡ ዘረኝነትም የለም ሰበዐዊነት እንጂ፡፡ በሚንሊክ አስተዳደር ወቅት ኢትዮጵያ ዘመናዊ በሚመስል ፌደራሊዝም ትተዳደር እንደነበር ስነቶቻችን እናውቃለን? አንዳንድ የሚንሊክን አላማ ለመረዳት እመቢ ባሉ መሳፍንት በቀር ከጦርነት በኋላ ሳይቀር ለእነዚያው የተዋጓቸው መሳፍንት ስልጣንን በሰጠት የራሳቸውን አካባቢ እንዲያስተዳድሩ ያደርጉ ነበር፡፡ በወቅቱ የተሸለ ግንዛቤ የነበራቸው እንደነ አባ ጅፋር የጅማው ያሉ የሚንሊክን አላማና ራዕይ ለመረዳት ስላልተቸገሩ በሠላም በአገር አንድ ማድረጉ ሂደት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

የሚንሊክ እውነተኛው ታሪክ ዛሬ ኢትዮጵያ ብለን የምንጠራትን አገር የፈጠሩ፣ አለም ላይ በእሳቸው ዘመን ኡሉ የተባሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ወደ አገር ያስገቡ እነዚህም ስልክ፣ ኤሌክትሪክ፣ መኪና፣ ባቡር፣ ሌሎችም፣ አገርን በዘበናዊ አስተዳደር እንድትመራ የዋቀሩ (ሚኒስቴር መሠረት ያደረገ) ሌሎች ብዙ በአንድ ሰው እድሜ ሊሰሩ የሚችሉ የማይመሰሉ ብዙ ራዕዮችን በተግባር ያስጀመሩ ናቸው፡፡ ይህን ሁሉ ማድረጋቸው ሳያንስ ሚንሊክን ከቅርብ ወዳጅ እስከ ሩቅ ባላአንጣዎቻቸው እጅግ ፈታኝ መነቆዎች ነበሩባቸው፡፡ በወቅቱ ባለው ኋላቀር አመለካከት ምክነያት ብዙ የቅርብ የተባሉ የቤተመንግስቱና የቤተክህነቱ ሰዎች እንቀፋቶች እንጂ ለሚንሊክ አጋዥ አልነበሩም፡፡ በሚንሊክ የአገር አንድ የማድረግም ሆነ አገርን ወደ ዘመናዊነት መቀየር ሂደት በተሻለ ወሳኝ ሚና የነበራቸው የውጭ አገር ሰዎችና አንዳንድ የቅርብ አባሮቻቸው ናቸው፡፡ ከቅር አባሮቻቸው ደግሞ በተለይም አገርን አንድ በማድረጉ ሂደት የሸዋ ኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝቦች ከየትኛውም የኢትዮጵ የሕብረተሰብ ክፍል ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡ የሸዋ ኦሮምኛ ተናጋሪ በታሪካዊው የአድዋው የሚንሊክ ድልም እንደዛው ከሌሎች በተለየ ነበር፡፡

ዛሬ ላለው አብዛኛው የኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ ግን የሚንሊክም ታሪክ እነዛ የሚንሊክ የቀኝ ክንድ የነበሩት ኦሮምኛ ተናጋሪ ሸዌዎችም የሚታየው በበጎ ሳይሆን በጥላቻ ነው፡፡ ምክነያቱ ደግሞ የታላቅ ባለራዕዮች ሕልም የማይገባቸው፣ በተንኮል የነወረ አእምሮ ይዘው ታሪክን በማጉደፍ ትውልድን በእነሱ በተመረዘ አእምሮ ለመበከል ያሰራጩት መርዝ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ለአሁኑ ትውልድ የበለጠ የታሪክ ትውስታና ክፉውም ደጉም ከሞላ ጎደል ከሚታወቀው የደርግና የኃ/ሥላሴ ዘመን ስህተቶች ይልቅ የሚንሊክ ዘመን ስህተትን አቅርቦና አግዝፎ ለማሳየት የተመረዙ አእምሮዎች የሚፈጥሯቸው ሀተታዎች ብዙ ናቸው፡፡ ምክነያቱ ግልጽ ነው አሁን ያለው ትውልድ የሚንሊክን ዘመን እውነተኛ ነገሮች በአካል የሚመሰክርለት የለውም ስለዚህ ምስክር በሌለበት በመሰሪዎቹ አእምሮው ሊመረዝ የሚችለው በቆየው ታሪክ እንጅ በአካል ያሉ መስካሪዎች ባሉበት ታሪክን ለመዋሸት ስለማይመች ነው፡፡ ሌላው ሚንሊክ የሠሩትን ታላላቅ ሥራዎች በበጎነቱ ማንሳቱ ራስን የሚያሶቅስ አደጋ ስላለው ነው፡፡ ዛሬ ላለው ትውልድ የሚንሊክ ዘመን ራዕይ ባለዕዳ አደርጎታልና ነው፡፡ በሚንሊክ ዘመን ራዕይ ይህች አገር ቀጥላ ቢሆን የት በደረሰች ነበር፡፡ ሌላው የሚንሊክ ራዕይ የአገር አንድነትና ብልፅግና ልዩ መሠረት ሥለነበር ይህንን መሠረት ሳያፈርሱ ስለዘረኝነት፣ ቀበሌ ዝቅ ብሎም ስለ ጎጥ እንዲያስብ ሕዝብን ማምከን አይቻልም፡፡

ዛሬ ከየትኛውም ክልል ትልልቅ ከሚባሉ ክልሎች በሚያሳዝን ሁኔታ የኦሮምያ ክልል በልማቱም ሆነ በመልካም አስተዳደሩ ወደ ኋላ መቅረቱ ግልጽ እየሆነ መጥቷል፡፡ መሠረታዊ ምክነያቱ ሕዝቡን ከሌሎች ጋርም ሆነ እርስ በእርስ ትብብር እንዳይኖረው የጥላቻን ዘፈን እየዘፈኑለት የራሳቸውን ኑሮ በተፈጠረላቸው አጋጣሚ እንደ ልባቸው የሚኖሩ ኦሮሞ ነን ባይዮች አደገኛ ዜጎች ናቸው፡፡ ይህንን ከሚያክል ትልቅ ክልልና ሕዝብ አይደለም ኢትዮጵያን ሊመራ የሚችል ክልሉን ሊመራ የሚችል ሰው ታጥቷል፡፡ ኦሮሞ ነኝ የሚለው አብዛኛው የዛሬው ትውልድ ትልቁ እርካታው የሌሎች መውደቅ በተለይም ነፍጠኛ እያሉ የሚጠሩት የአማራውና አሁን በስልጣን ላይ በብዛት እንደተወከለ የሚነገርለት የትግራይ ሕዝብ ውድቀት እንጂ የራሱ ብልጽግና አይደለም፡፡ ለኦምኛ ተናጋሪው ክልል በልማትና በአስተዳደር ወደ ኋላ መቅረት ቁጭት ተሰምቶት ሊሰራ ከሚሞክር መሪና ትውልድ ይልቅ ከብዙ አመታት በፊት የተፈጠሩ የታሪክ ስሕተቶች ደግሞደጋግሞ በማላዘን ሌላ መርዛማና በጥላቻ የተበከለ ትውልድ ለማዘጋጀት ተግቶ የሚሰራው በዝቷል፡፡

ዛሬ ኦሮምኛ ተናጋሪ ሆኖ ያለው ሕዝብ በዘር (በደም) አንድ እንዳልሆነ ግልጽ ነው፡፡ በደም ግንድ ከሆነ የወለጋና ሐረር ኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ ከሚቀራረበው በላይ የጎጃ አማርኛ ተናጋሪውና የወለጋ ኦሮምኛ ተናጋሪው ይቀራረባሉ፡፡ የባሌና ሸዋ ኦሮምኛ ተናጋሪዎች ከሚቀራረቡት በላይ የሸዋ ኦሮምኛ ተናጋሪና የሸዋ አማርኛ ተናጋሪ የበለጠ የደም ትስስር አላቸው፡፡  በባህልም ቢሆን እንደዚያው ነው፡፡ ዛሬ ዘረኝነትንና የቀበሌ አስተሳሰብን የሚሰብኩ ግን ቋንቋን ተመርኩዘው ግዙፉን ሕዝብ በአንድ ከአጨቁትና ከሌሎች ጋር ሕብረት እንዳይኖረው ከአወሩት በኋላ ወደታች ደግሞ በጎሳና፣ ቀበሌ፣ ዝቅ ብለው በጎጥ ይሸነሽኑታል፡፡ የኦሮምኛ ተናጋሪው ሕዝብ ከሌሎች በአካባቢው የሌላ ቋንቋ ተናጋሪዎች ያልተጋጨው የለም፡፡ ምክንያቱ ግልጽ ነበር፡፡ ሕዝቡ ለሌሎች ጥላቻ እንዲኖረው ስለሚሰበክ ነው፡፡ አልፎም ይሄው መለያየትን የሚሰብከው መዝሙር እርስ በእርስ ሳይቀር ጥላቻንና ግጭትን አስነስቶ አይተናል፡  እንደወንድማማች የሚተያዩት ጉጂና ቦረናን ሳይቀር ለከፍተኛ ደም መፋሰስ ዳርጓል፡፡

ይሄው ሃያ ምናምን አመት ሙሉ ስለቀድሙት ገዥዎች ጭቆናና በደል ሲነግሩን፡፡ የቀደሙትስ ጨቋኝና ጨካኝ ሆነው የኦሮሞን ሕዝብ ሲበድሉት ኖሩ ተብሎ ይታሰብ ዛሬስ የዚያን ዘመን በደል ሊያስረሳ የሚችል መሪ እንዴት ከዚህ ትልቅ ሕዝብ መካከል ጠፋ፡፡ እውነታው የቀደሙት ጨካኝና በደል አድርሰውም ከሆን ለኦሮምኛ ተናጋሪው የተለየ አልነበረም፡፡ ብዙ የኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ አማርኛ ተናጋሪ ከነበረው ይልቁንም የነገስታቱ ወገን ነው ተብሎ ከሚታመነው የሸዋ አማርኛ ተናጋሪ ሕዝብ በቀድሞ ነገስታት የተሻለ ተጠቃሚ እንደነበር እናውቃለን፡፡ ሌላው ቀርቶ የነገስታቱ የቅርብ አጋር እየተባለ ዛሬም ድረስ በሌላው የኦሮምኛ ተናጋሪ በጥሩ አይን የማይታየው የሸዋው ኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ በነገስታቱ ዘመን አንዳች ተጠቃሚ እንዳልነበረ አእምሮ ካለን እናስተውላለን፡፡ ለእነዚህ ሕዝቦች ከሌላው በተሻለ የቀረላቸው ሀብት ቢኖር ሌላውን በጥላቻ አለመመልከት ለአገር አንድነትም ልዩ ፍቅር መኖር ነው፡፡

ሌሎች ክልሎች በአቅማቸው ልማታቸውንና የአስተዳደርም ችግራቸውን በፍታት ልዩ መንገድን እየሄዱ ይገኛሉ፡፡ በተለይም የቀድሞው ገዥና ጨቋኝ ተብለው የተፈረደባቸው የአማርኛው ተናጋሪ ሕዝብ ክልል  በቁጭት በሚመስል ሁኔታ እያደገ ለመሆኑ ግልጽ እየሆነና ልዩነቱንም ከሌሎች እያሰፋ መሆኑን እያሳየን ይገኛል፡፡ ትግራይ የገዥውን መንግስት ድጋፍ እያገኝ ስለሆነ ነው እየተባለ ቢታማም እውነታው የእድገት ጥማት ባላቸው መሪዎች ምክነያት እንጂ የማዕከላዊው መንግስት ተፅዕኖ ብቻ እንዳልሆነ እናያየለን፡፡ ደቡብና ሌሎች አናሳ እይተባሉ የሚጠሩ ክልሎች ሳይቀር ከኦሮምያ በተሻለ ዕድገት እያሳዩ ናቸው፡፡ በማዕከላዊውም መንግስት ያላቸው ተሳትፎ ከኦሮምያ ይልቅ የደቡብ የተሻለ እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡ ምክነያቱ ግልጽ ነው ኦሮምያ ኢትዮጵያን በሚወክል አመለካከት ይቅርና ክልሉን እንኳን በሚወክል አመለካከት የተገነባ ሰው ታጥቶበታል፡፡ በደቡብ ብዙ ሕዝቦች ኢትዮጵያዊ መሠረትን በደንብ ያደበሩ ናቸው፡፡ በኦሮምያ  ሌሎችን በመጥላት የተጀመረው ሂደት ዛሬ ወርዶ ቀበሌ ደርሷል፡፡ ወለጋው ወለጋውን፣ አርሲው አርሲውን፣ ታች ወርዶ ደግሞ ሻንቡ ሀረቶ ምናምን እያለ የሚከፋፍል ነው፡፡ ይህ አይነቱ ባሕሪ በሌሎች ክልሎች አይንጸባረቅም ሳይሆን በንጸባረቅም ሌሎች ሌሎችን ጨምረው በሚያማክሉ ከፍተኛ ባለአእምሮዎች ይመክንና ቀበሌ ከሆነ ቀበሌ፣ ከፍ ብሎ በክልልም ከሆን ክልሉን ሳያልፍ ይመክናል፡፡ ኦሮምያ ግን እንደዚያ አይደለም፡፡ የወረደውን የጎጠኝነት ስሜትና አመለካከት የሚያመክን ጠፍቶ ትውልዱ በአብዛኛው በወረደው ጎጠኝነት ስሜት መክኗል፡፡

አሳዛኙ ነገር ተማርን የተሸለ የሕወት ልምድ አልን በሚሉት ይህ የአመለካከት ወርደት በርትቷል፡፡ በተለይም ደግሞ በተለያዩ መንገድ ወደ ውጭ ሄዶ በሚኖረው የኦሮምኛ ተናጋሪው ለሌሎች ያለው ጥላቻ እጅግ የከፋ ነው፡፡ አማራ ወይም ትግሬ የሚባለውን በመጥላት ሌሎችን ይጋብዛል፡፡ ሌሎችንም ወንድም እንደሆነ ሊሰብክ ይሞክራል፡፡ ይህ ጥላቻን ያዘለው ስብከት ከትልቋ ኢትዮጵያ እስከ ታች ተራ ግለሰቦች ላይ ያነጣጠረ ነው፡፡ በቅርቡ በቴዲ አፍሮ ምክነያት የበደሌን ቢራ ላለመጠጣት የተደረገው አድማ አንዱ ሕዝቡ እንዴትና በምን አይነት አመለካከቶች እንደሚመራ በሌላውም ላይ ያለው ጥላቻ ምን ያህል እንደሆነ ያመላከተ ነበር፡፡  ይህን ለሚያሕል አደማ ደግሞ ያደረሰው በሌሎች ከፍተኛ አደናቆትን ያተረፈው የቴዲ አፍሮ  ጥቁር ሰው የሚለው ዘፈኑ እንደነበር ግልፅ ነው፡፡ የቴዲው ጥቁር ሰው ሚንሊክ ግን ለአፍሪካ ሳይቀር ኩራት እንጂ የሚያሳፍር አልነበረም፡፡ በጥላቻ የተመረዘው የእኛው ኦሮምኛ ተናጋሪ ግን ያንን የጥቁር ሕዝብ ሁሉ ክብር የሆነውን ታሪክ ለመስማት አለመፈለግ ብቻም ሳይሆን ያንን ታሪክ የሚያነሱትን በሚያገኘው አጋጣሚ ሊበቀል እንዳለው አየን፡፡ አሁን ያለው እንዲህ የተመረዘው የኦሮምኛ ተናጋሪ ትውልድ ግን ስለሚንሊክም ሆነ በዘመኑ ስለነበሩ ክስተቶች በውል የሚያውቀው ነገር የለም መርዛማና የራሳቸውን ልዩ ፍላጎት በሕዝቡ ሊያሳኩ የሚያሴሩትን ስብከት ተቀበለ እንጂ፡፡

በቅርቡ የሀረካ ሙራ ሐርማ ሙራ መታሰቢያ በሚል አንድ ሐውልት ተመርቋል፡፡ እኔ እውነትም ይህ ክስተት በየትኛውም ስህተት ቢሆን ተከስቶ ከነበረ መታሰቢያ መቆሙ ክፋት አለው ብዬ አላምንም፡፡ ሆኖም ክስተቱ ተፈጠረ ከተባለ ከስንት ዘመን በኋላ ዛሬ ሀውልት ለማቆም የታሰበበት አላማ ያንን ክስተት ለማስታወስ የተደረገ ሳይሆን ይልቁንም ጥላቻን ለማጠናከር እንዲህ ያደረገሕ ሕዝብ ነበር ለማለት የቆመ ሀውልት ሆኖ ነው የተሰማኝ፡፡ አሁን አሁን እንደውም ያ አሳቃዊ ክስትት ሆን ተብሎ የተፈጠረ ታሪክ ነውም ብዬ እየተጠራጠርኩ ነው ከሌሎች ጋር ጥላቻ እንዲፈጠር የሚደረገው ሴራ ብዙ ነውና፡፡  ይህ ሀውልት በተመረቀበት በዚህ ሰሞን የሩዋንዳውም እልቂት ሃያኛ ዓመት የሚታሰበበት ነበር፡፡ ሲታሰብ ግን ልዩ መልዕክት የነበረው የተፈጠረውን ክስተት የሚያስረሳ ሰላምንና የአገር ብልጽግናን በዚያች አገር የማምጣት ራዕን ነው፡፡ ሐውልት እነኳን ለእነዚያ ዜጎች መታሰቢያ ማቆም ቢያስፈልግ ዳግም እንደዚያ ያለ አረመኔነት በዚያች አገር እንዳይከሰት ለትውልድ ማስተማሪያነት እንጂ ቂም በቀለኝነትን ለማቆየት አይሆንም፡፡ የኦሮምያው የሀርካ ሙራ ሐርማ ሙራ ሐውልት ግን ግልጽ መልዕክቱ ሌሎችን በመጥላት የተመረዘውን ብዙ የኦሮምኛ ሕዝብ የበለጠ ጥላቻ እንዲያድርበት ሌሎችም ሌሎችን በመጥላት ተሳትፎ እንዲያደርጉ የታለመ ነው ብዬ አመንኩ፡፡

ብዙ የኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ በኢትዮጵያ ታሪክም ሆነ የወደፊት ብሩሕ ራዕይ ደስተኛ አይደለም፡፡ እነዚህ የሕዝቡ አካላት የኢትዮጵያን ውድቀት እጅግ የሚመኙ ናቸው፡፡ ሌላ ቀርቶ ከኢትዮጵያ ጋር የተያያዘ ወይም እነሱ በጣም ከሚጠሉት አማራ ወይም ትግሬ ከሚባለው ሕዝብ ጋር የተያያዘ የራሳቸው ነገር እንኳን እርም ነው፡፡ የአባይ ወንዝን እንደምሳሌ ላንሳው፡፡ የአባይ ወንዝ ከኢትዮጵያ ጋር በተያያዘ ብዙ ይነሳል፡፡ መነሻው ደግሞ ጎጃም የጮቄ ተራራ ነው፡፡ ሆኖም አባይን በውል የምታውቁት ካላችሁ አባይን አባይ ያደረገው የጮቄ ተራራ ወይም ከጣና የቀዘፈው ውሀ ሳይሆን ከኦሮምያ የሚነሱ ታላላቅ ወንዞች ናቸው፡፡ በተለይም ደዴሳና ዳቡስ፡፡ ይሄንን ለማስተዋል አሁን ግድብ እየተሰራበት ያለውን ቦታ የሚፈሰውን ውሃና ወደጎጃም ስትሻገሩ የምታዩትን ውሃ አስተውሉ፡፡ ግብጾቹም ይሁኑ ሌሎች እንቅልፍ የሚነሳቸው ጎጃም ያያችሁት አባይ አይደለም ደቡስና ዴዴሳ የደለቡት አባይ እንጂ፡፡ የአባይ ሥም ሲነሳ ግን ብዙ የኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ ጥሩ ስሜት የለውም፡፡ ግድቡን ጨምሮ ሌሎች ለኢትዮጵያ ብልጽግናም ትልቅ ድርሻ ያላቸው ልማቶችም እንዲሁ በብዙ የኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ በመልክም አይታዩም፡፡ ግን ለምን? የሚንሊክን ታሪክና ዘመን እንዲህ በጥላቻ የሚያስመለክትስ በእውን የተጨበጠ ይቅር የማያሰኝ ስህተት አለ? ካለስ ይህ ትውልድ እነዴትና በምን ምክነያት እነዚያ ስህተቶች እንደተከሰቱ ምን ያህል ተረድቶ ነው እንዲህ በጥላቻ የተመረዘው?! ነው ወይስ አሁንም እያየን እንዳለንው የኢትዮጵያ ነገር ስለማያደስተው ከኢትዮጵያዊነት ጋር የተቆራኘውን የአገሪቱን መስራች ሚንሊክን በስሜት ብቻ መጥላት ይሆን?

ኦሮምያ ውስጥ ባለፉት ሃያ ምናምን አመት ከተከሰተው ግፍ በላይ በቀደሙ የታሪክ ጊዜያት ለመከሰቱ ጥያቄ እያጫረብኝ ያለ ጉዳይ ነው፡፡ ብዙ ጥያቄዎች አሉ! ኦሮምያ የሚባለውም ክልል ይሁን ኦሮምኛ ተናጋሪ የተባለው ሕዝብ ግልጽ በሚታይ ሁኔታ እየተቀደመ እንደሆነ ይረዳ፡፡ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ይህ ልዩነት ጎልቶ ሲታይ ይህችን መልዕክቴን ያነበቡ ያስታውሱ ይሆናል፡፡  ግን ለምን???!!

የታላቋ ቀን ልጅ ሚያዝያ 1 2006 ዓ.ም.

 

ሕገመንግስት፤ መብት ተረጋግጧል ወይስ ተረግጧል (ተክለሚካኤል አበበ)

$
0
0

የማርቆስ ብዙነህ ደብዳቤ፤

ተክለሚካኤል አበበ)

ተክለሚካኤል አበበ)

1-      “በርካታ ትምህርት ቤቶች፤ ዩኒቨርስቲና የመንግስት ተቋማት በሚገኙበት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የማይቻል በመሆኑ፤ የተጠየቀው የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑን እንገልጻለን” ይላል፤ በአዲስ አበባ መስተዳድር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቅ ክፍል ሀላፊ፤ በአቶ ማርቆስ ብዙነህ ማንደፍሮ፤ መጋቢት 23 ቀን 2006/2014 የተፈረመው ደብዳቤ፡፡ አንድነት፤ ሰልፉን ለማድረግ ያቀረባቸው መስመሮች 3 ሲሆኑ፤ ሶስቱም መስመሮች ከቀበናው የአንድነት ጽ/ቤት ይነሳሉ፡፡ አንደኛው መስመር በአራት ኪሎና በፒያሳ አድርጎ፤ ወደ አዲስ አበባ መስተዳድር ጽ/ቤት ያመራል፡፡ ሁለተኛው አማራጭ በአራት ኪሎ ተጉዞ፤ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን አልፎ መስቀል አደባባይ ያበቃል፡፡ ሶስተኛው አማራጭ፤ በአራት ኪሎ ፒያሳ፤ ቸርችልን ይዞ ድል ሀውልት ጋር ያበቃል ነበር የሚለው፡፡ ከላይ እንደተመለከታችሁት፤ የአዲስ አበባ መስተዳድር፤ ሶስቱም አማራጮች አልተመቹትም፡፡ የተመረጡት መስመሮች በርካታ ትምህርት ቤቶች የትምህርትና የመንግስት ተቋማት ስለሚገኙበት፤ አንዳንዶቹ ደግሞ ግንባታ ያለባቸው መንገዶች ስለሆኑ፤ እንዲሁም በእለቱ የህዳሴው ግድብ ግንባታን የተመለከቱ ዝግጅቶች ስላሉ፤ መስተዳድሩ ሰልፉን ሳይፈቀድ ቀረ፡፡

2-     አንድነት ክልከላው ሕገወጥ ነው፤ ሰልፋችንን እንቀጥልበታለን ብሎ አቋሙን ሲያሳውቅ፤ የአዲስ አበባ መስተዳድር ዘግይቶም ቢሆን፤ ተለዋጭ ቀንና መንገድ እንደሚቀበል ጠቆመ፡፡ ወትሮም ቢሆን የአዲስ አበባ መስተዳድር የተከተለው ስልት የማዳከም፤ የማበሳጨት፤ የማሰናከልና ተስፋ የማስቆረጥ እንጂ ጨርሶ የመከልከል አይመስልም፡፡ ስለዚህም ድርጅቱ በተዘጋጀበትና በመረጠው ቀን ባይሆንም፤ በሌላ ቀን እንዲሆን ለመለወጥ አስገደደ፡፡ በርግጥ የአዲስ አበባ መስተዳድር የመጀመሪያውን ሰልፍ ያሰናከለበት ምክንት አግባብ ባይሆንም፤ የአንድነት ልሳን ፍኖተ-ነጻነት፤ የአዲስ አበባ መስተዳርን የዘገየ እሺታ አስጩሆ የዘገበበት መንገድ ብልሀት ይጎድለዋል፡፡ ፍኖት ነጻነት፤ “በመጨረሻ የአዲስ አበባ መስተዳድር እጅ ሰጠ” ነው ያለው፡፡ ይሄ አይነቱ ረታናችሁ፤ አሸነፍናችሁ አካሄድ መንግስት የሚያሸሽ ስለሆነ፤ ፍኖተ ነጻነት ከዚህ አይነቱ አናዳጅ ርእሰ-ዜና መራቅ አለበት፡፡ ኢሳትም ይሄን አይነት ሰራንላችሁ፤ የታባታችሁ የሚል አዋራጅ አዘጋገብ አልፎ አልፎ ይተገብራል፡፡ ፈጣሪ ጊዜና ጉልበት ከሰጠኝ፤ ይሄ አይቱ ጠላትን የማዋረድና የጽንፈንነት አካሄድ ለምን እንደሚጎዳ እጽፋለሁ፡፡ ለጊዜው የፍኖተ ነጻነት ርእስ እንዳልተመቸኝ ሳልጠቅስ አላልፍም፡፡

 

ስለሕገመንግስት፤ መብት ተረጋግጧል ወይስ ተረግጧል

3-     የሆነ ሆኖ፤ ወደሰልፉ ጉዳይ ስንመለስ፤ አሁን በስራ ላይ ባለው የኢትዮጵያ ሕገመንግስት መሰረት፤ ዜጎች በመሰላቸው ርእስ፤ በጣማቸው ምክንያት፤ በታያቸው ሕልም፤ በተሰማቸው ደስታ፤ ባሳዘናቸው ሰበብ፤ መንግስትን ደግፈውም ይሁን ተቃውመው፤ ሀሳባቸውን በተቃውሞ ወይም በድጋፍ የመግለጽና የመሰብሰብ መብታቸው ተረጋግጧል፡፡ ሕገ-መንግስቱ ራሱን በራሱ ያስፈጽም ይመስል፤ ሕወሀት/ኢህአዴግ ብዙውን ግዜ እንዲህ ያለው መብት በሕገ መንግስቱ ተከብሯል፤ በሕገመንግስቱ ተረጋግጧል እያለ የሚያጭበረብረው ነገር ስላለ፤ ይሄንን የተቃውሞ ሰልፍ በህገመንግስቱ ተከብሯል የሚል አረፍተነገር የተመለከተ ሰው፤ ጥንቃቄ ካላደረገ በስተቀር በሀይለኛው ይሳሳታል፡፡ በሕገ መንግስቱ መሰረት፤ ተረጋግጧል የሚለው ቃል፤ ተከብሯል በሚለው መተርጎም ቢኖርበትም፤ በኢትዮጵያ በተግባር እንደምናየው ግን፤ ተከብሯል በሚለው ሳይሆን፤ በሕገመንግስት ተረግጧል በሚለው ቢተረጎም ይቀላል፡፡ መብቱ በሰበብ አስባቡ ተሸራርፏል፡፡ በአንድነትና በሰማያዊ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ላይ የሚደርሰውን ለተመለከተ ይሄንን መረዳት አያዳግተውም፡፡

4-     ለምሳሌ ሕገመንግስቱ ሰልፍ ከማድረግ በፊት ለሚመለከታቸው አካላት ስለማሳወቅ ብቻ ሲናገር (የአቶ ማርቆስ ብዙነህ ማህተም የሰልፍና ስብሰባ ማሳወቅ ኦፊሰር ነው ይላል)፤ ህግ አውጪዎቹና አስፈጻሚዎቹ ደግሞ፤ የለም ሰልፍ አሳውቅ ሳይሆን አስፈቅድ ነው ብለው ተረጎሙት፡፡ መተርጎም ብቻ ሳይሆን፤ ሕገ መንግስቱ ያረጋገጠውን መብት፤ ሰልፍን የተመለከቱ አዋጆችና ደንቦች አውጥተው ረጋገጡት፡፡ ለምሳሌ የአዲስ አበባ መስተዳድር የስብሰባና ሰልፍ አሰራር ስነ-ስርአት አንቀጽ 5.1 ከላይ በተጠቀሱት የመንግስትና የትምህርት ተቋማት አካባቢ ሰልፍ ማድረግ አይቻልም ይላል፡፡ በካናዳ ቢሆን፤ እነዚህን ሕገመንግስታዊ መብት የሚሸራርፉ አዋጆችና ደንቦች፤ ፍርድቤቶች ዋጋ የለሽ ህጎች ብለው ይወስኑባቸው ወይም ያመክኗቸው ነበር፡፡ እኛ አልታደልንምና፤ እስካሁን እንዳየነው፤ የኢትዮጵያ ፍርድቤቶች እንዲህ ያለውን ሕግ የመሻር ወይም፤ ሕገመንግስቱን ይጥሳል ብለው የመወሰን ስልጣንም ወኔውም አልተመለከትንባቸውም፡፡ ከተመለከትንም፤ ወይ ፍርዱ ወይ ዳኛው አይጸናም፡፡ መንግስት እንዲህ ነው ካለ፤ የኢትዮጵያ ፍርድቤቶችም አብረው እንዲያ ነው ይላሉ፡፡ ከመንግስት ጋር ይስማማሉ፡፡

 

የት ሄደን እንሰለፍ፤ ነው ወይስ እንሰየፍ

5-     ሰልፍ 48 ሰዓት ቀደም ብለህ አሳውቅ የሚለው ድንጋገጌ ሰልፍ አስፈቅድ በሚለው አዋጅ ተሸርፎ ብቻ አላቆመም፡፡ ከአንድነትና መኢአድ እንዲሁም ሰማያዊ ፓርቲ ስኬታማ ሰልፎች በኋላ ደግሞ ሰሞኑን የምንመለከተው፤ ጭራሽኑ ሰልፍ መሰለፊያ ስፍራ የሚያሳጣ ሁኔታ እንዳለ ነው፡፡ ቀደም ሲል ሰልፍ የተከለከለባቸው ስፍራዎች የጦር ሰራዊት ካምፖች፤ ሆስፒታሎችና መሰል ስፍራዎች ነበሩ፡፡ ከሰሞኑ ደግሞ በትምህርትቤቶች ወይም ዩኒቨርስቲዎች አካባቢም ሰልፍ ማድረግ አይቻልም የሚል ደንብ ወጣ፡፡ ቀጥሎ በእምነት ተቋማት ማለትም በመስጊድና በአብያተክርስቲያናት አካባቢ አይቻልም የሚል አዋጅ/ደንብ ይመጣል፡፡ በአዲስ አበባ በሁሉም ማእዘን ቢኬድ፤ ትምህርትቤት ባይኖር፤ ሆስፒታል አለ፤ ሆስፒታል ባይኖር፤ የጦር ካምፕ አለ፤ የጦር ካምፕ ባይኖር፤ ቤተ-እምነት አለ፤ ቤተ-እምነት ባይኖር፤ ዩኒቨርስቲ አለ፤ ዩኒቨርስቲ ባይኖር መዋእለ-ሕጻናት አለ፤ ያም ባይኖር የሆነ ነገር አለ፡፡ ስለዚህ አዲስ አበባ ውስጥ ሰለፍ ሊደረግ የሚችልባቸው ስፍራዎች ውሱን በጣም ውሱን ሊሆኑ ነው፡፡ ደግሞስ የተቃውሞ ሰልፍ አንድም መንግስት እንዲሰማው ለማድረግ ሆኖ ሳለ፤ በመንግስት ተቋም በጠገብ መሰልፍ አይቻልም የሚሉት ደንብ እንዴት ያለ ደንብ ነው፡፡ ተቃጠልን እኮ ጎበዝ፡፡

 

የአንድነት የሶስት ወር ዘመቻ

6-    እንግዲህ በዚህ ሁሉ ሕገመንግስቱን የሚሸራርፉ የተጻፉ ደንቦችና አዋጆች፤ ያልተጻፉ አፋናዎችና ትንኮሳዎች ውስጥ ተሸሎክሉከው ነው፤ አንድነቶችና ሰማያዊዎች የተቃውሞ ሰልፎችን የሚያደርጉት፡፡ አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ፤ (ከዚህ በኋላ አንድነት እያልኩ ነው የምጠራው)፤ በቀጣዮቹ ሶስት ወራት ውስጥ ከአዲስ አበባ ተጀምሮ አዲስ አበባ የሚያበቃ፤ በ15-17 ከተሞች የሚደረግ፤ የኑሮ ውድነትን፤ የሰብአዊ መብት ጥሰትና አፈናና፤ የመሬት ባለቤትንትን፤ የሚመለከቱ የተቃውሞ ሰልፎችን አሰናድቷል፡፡ አንድነት በተለያዩ ከተሞች ውስጥ የሚደርጋቸውን ሰልፎች በገንዘብ ለመርዳት በውጭ አገር የሚገኙ የተለያዩ ከተሞች ኢትዮጵያዊያን ቃል እየገቡ ነው፡፡ መቼም ሲያትል ጎንደሬ ይበዛል፤ ጎንደርን ወስዷል፡፡ አትላንታ አንድ ከተማ ወስዷል፡፡ ላስ ቬጋስም እንደዚያው፡፡ እስካለፈው ወር መጨረሻ ድረስ የቀሩት ከተሞች አምስት ብቻ ናቸው፡፡ የቶሮንቶ አንድነት የድጋፍ ሰጪ ማህበርም የነቀምት ከተማን ሰለፍ ለመርዳት ቃል ገብቷል፡፡ ቀደም ሲል እሁድ ማርች 23 ቀን የአንዱዓለም አራጌን መጽሀፍ ለማከፋፈልና እስረኞችን ለማሰብ በተጠራ ዝግጅት ላይ የዝግጅቱ አስተባባሪ አቶ ታምራት ይገዙ ቶሮንቶ መቀሌንም ስፖንሰር እንደሚያደርግ አስታወቋል፡፡ ስለዚህ፤ ቶሮንቶ ሁለት ከተሞችን ስፖንሰር ያደርጋል ማለት ነው፡፡ ይሄ በረከት ሲያንሰን ነው፡፡

 

እነሆ ቅስቀሳ፤ አጋርነት ለነቀምት፤

7-     አንድነት ቶሮንቶ፤ ለነቀምቱ ሰልፍ የሚሆን ገንዘብ ለማሰባሰብ እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር ቅዳሜ ኤፕሪል 26 ቀን፤ ከሰዓት በኋላ፤ ከ3pm ሰኣት ጀምሮ፤ 2050 ዳንፎርዝ ጎዳና ላይ በሚገኘው ሂሩት ካፌ፤ የአብረን እንዋል መርሀግብር አዘጋጅቷል፡፡ ይሄ ጽሁፍ በከፊል የዚያ ዝግጅት ቅስቀሳ አካል ነው፡፡ ልቀስቅሳችሁ ተዘጋጁ፡፡ ቅስቀሳው እንዲህ የሚል ነው፤ አገር ቤት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን፤ ከላይ የጠቀስናቸውን መሰናክሎች አልፈው የተቃውሞ ሰልፍ ለማዘጋጀት ደፋ ቀና ሲሉ፤ ሰልፋቸው በኢህአዴግ ሰራዊት ወይም ፖሊስ ወይም ደህንነቶች እንጂ፤ በገንዘብ እጦት ምክንያት እንዳይሰናከል የማድረግ ግዴታ አለብን የሚል ነው፡፡ በቶሮንቶ አካባቢ የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን፤ በዚህ መደበኛ ባልሆነ፤ የአብረን እንዋል ዝግጅት ላይ በመገኘት፤ የበኩላችንን የገንዘብ ልገሳ እንድናደርግ ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ፤ ቅዳሜ ኤፕሪል 26 ቀን፤ 2014 ዓ.ም፤ ከሰኣት በኋላ፤ ሂሩት እንገናኝ፡፡

8-     በነገራችን ላይ፤ ቶሮንቶ በቆየሁባቸው ያለፉት 13 ወራት፤ ከገንዘብ ማሰባሰብ ጋር በተያያዘ ቶሮንቶ የሚንቀሳቀሰው ከአቅም በታች ነው ማለት ይቻላል፡፡ ትንሽ ቋጣሪ መስሎብኛል፡፡ በርግጥም በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ በሚደረጉ ፖለቲካ ነክ ዝግጅቶች ላይ የሚታደሙትንና ያላቸውን የሚወረውሩት ቸሮች፤ ተመሳሳይና የተወሰኑ ሰዎች በመሆናቸው፤ የዚህ ከአቅም በታች የመንቀሳቀስ ተጠያቂዎች እነማን እንደሆኑ እንጃ፡፡ ላለፈው ስርየት ሆኖ፤ ስለሚመጣው ሳስብ ግን፤ እኔ እንዲህ ያለውን አገራዊ ዝግጅት የማየው እንደበረከት ነው፡፡ ይሄ በረከት ለሁላችሁም መድረስ አለበት፡፡ ስለዚህ የመጪው ኤፕሪል 26፤ የአንድነት በረከት እንዳያመልጣችሁ፤ ሂሩት ካፌ እንገናኝ፡፡ በእለቱ በተለያየ ምክንያት መገኘት ያልቻለም፤ የገንዘብ ልገሳውን በሰው መላክ እንደሚችል ወይንም በአንድነት ባንክ ሂሳብ Unity for Human Rights and Democracy: TD Trust; የባንክ ሂሳብ ቁጥር፡ 12682 0041 0883 5209213 መክተት እንደአማራጭ እንደተቀመጠ፤ አንድነት ቶሮንቶ ያወጣው መግለጫ ያሳያል፡፡

 

ከደሴ ወደአዲስ፤ … ወደነቀምት፤ በዚህ 22 አመት እንደነቀምት የተጎዳ ማን አለ፤

9-    በርግጥ የአንድነት የአዲስ አበባ ሰልፍ በተያዘለት ቀን መጋቢት 28 አልቀጠለም፡፡ ይሄ ጽሁፍ ወደህትመት ሲላክ፤ የአዲስ አበባው ሰልፍ ሚያዚያ 5 እንደሚደረግ ቢገመትም፤ አሁን ዘግይቶ በደረሰን ዜና ደግሞ፤ የአዲስ አበባ መስተዳድር ሰልፉ ቅዳሜ፤ የሰልፉም አቅጣጫ ወደጃንሜዳ ካልሆነ እያለ ነው፡፡ ማደናበር፤ ማናደድ፤ ማዘናጋት ይሉታል ይሄንን ስልት፡፡ እኔ፤ ብልጥ ልጅ የሰጡትን ይዞ ያለቅሳል ነው የምለው፡፡ ፖለቲካና ሕይወት ,ባልመረጥነው መንገድ ውስጥ የመረጥነውን ለማግኘት የምናደርገው ሩጫ ነውና፡፡ መጋቢት 28 ቀን በደሴ የተደረገው ሰልፍ ደማቅና የሚያበረታታ፤ በርግጥም ለሌሎች ከተሞችም መነሳሳትን የሚያመጣ እንደሆነ አስተውያለሁ፡፡ ስለዚህ፤ ነቀምትን ከደሴ የተሻለ ለመቀስቀስና ለማሰለፍ፤ ሁላችንም መረባረብ እንዳለብን ቀስቃሽ አያስፈልገንም፡፡ ደግሞስ በዚህ 22 አመት በኦነግ ስም እንደነቀምት የተጎዳ ማን አለ፡፡ ስለዚህ ነቀምት ተሰልፎ እሪይ ይል ዘንድ ግድ ነው፡፡ ደሴ ነቅሎ ወጥቷል፡፡ ነቀምትም ነቅሎ ይወጣል፡፡ ነቀምት ነቅሎ እንዲወጣም እኛም ከዚህ ከቶሮንቶ ነቅለን እንወጣለን፡፡ ቅዳሜ፤ ሚያዚያ 26 ቀን፤ ከሰዓት በኋላ፤ ከ3 እስከ 6 ሰዓት ሂሩት እንገናኝ፡፡

10-    ለተጨማሪ የአንድነት ዝርዝር አገልግሎቶችና መረጃዎች በአካል በአንድነት በጽህፈት ቤታት፤ ወይም ከታች በተጠቀሱት የመገናኛ መንገዶች ያግኙን፡፡ አንድነትን ለማግኘት፤ ኢሜል፤ unityforhumanrights@gmail.com ፤ ድረገጽ፤ http://andnettoronto.blogspot.ca/. የጽህፈት ቤት አድራሻ፡ B2- 2017 Danforth Avenue, Toronto, ዳንፎርዝ ላይ፤ ከዉድባይን ባቡር ጣቢያ በስተምስራቅ 50 ሜትር ራቅ ብሎ፤ ከዘመን እንጀራ መደብር በተቃራኒ፤ ከትብብር መረዳጃ እድር ጎን፡፡

ተክለሚካኤል አበበ ነኝ፤ ቶሮንቶ፤ ሚያዚያ፤ 2006/2014

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live