Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ከአገር መውጣት የማይችሉ ባለሥልጣናት በጭንቀት ውስጥ ናቸው

$
0
0
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
stressed-948x472ኢህአዴግ በሙስና ስም የ”ማጥራት ዘመቻ” ማካሄዱን ተከትሎ የተከሰተው አለመተማመንና እርስ በርስ በጥርጥር የመተያየት ችግር ካድሬውን ማስጨነቁ ተጠቆመ። ኢህአዴግን ለመሰናበት የሚፈልጉ በርካታ ካድሬዎች “ለምን” በሚል የሚቀርብላቸውን ጥያቄ በመፍራት የግድ ፓርቲውን መስለው እንደሚኖሩ ተገለጸ።

የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ቀደም ሲል ኢህአዴግን ተሰናብተው የወጡና በተለያዩ የውጪ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው በማገልገል ላይ ካሉ ያገኘውን መረጃ በመጥቀስ እንደዘገበው፣ የቀድሞ የትግል ጓደኞቻቸው “በደህና ጊዜ ተገላገልክ” በሚል በፓርቲው ውስጥ ችግር ስለመኖሩ እየነገሯቸው ነው። አብዛኞቹ ኢህአዴግን ተለይተው በሰላም ስለመኖር እንደሚያስቡ ነው የተሰማው።

 

የቤተሰቦቻቸው የወደፊት እድልና የነሱ በፍርሃትና በጭንቀት መኖር አሳዛኝ እንደሆነ የነገሩት የቀድሞ የኢህአዴግ ሰዎች “አሁን ያለው ኢህአዴግ በቀለም ቀቢ የተዋበ ይመስላል” በማለት አንድ በሚኒስትር ዲኤታ ማዕረግ እያገለገለ ያለ የቀድሞ ጓደኛቸው እንደነገራቸው ገልጸዋል።

 

ለስራ እንኳን ካገር መውጣት የማይችሉ ባለስልጣኖች እንዳሉ ዘጋቢያችን አመልክቷል። በተቀመጡበት ሃላፊነት ወደ ውጪ የሚያስኬድ አጋጣሚ ሲኖር የሚከለከሉ እንዳሉም ያገኛቸውን መረጃዎች ጠቅሶ ዘግቧል። ለሃላፊዎቹ ደህንነት ሲባል የሚሰሩበትን ተቋምና ስም መናገር እንደማይችሉ በመጥቀስ መረጃውን የሰጡት ክፍሎች “ባለስልጣኖቹ በመካከላቸው እርስ በርስ መተማማን ስለማይችሉ ችግራቸውን መወያየት እንኳን አይችሉም” ብለዋል፡፡

 

“በጣም የሚቀርቡኝ ጓደኞቼ ገንዘብ ወደ ውጪ እንድወስድላቸው እስከመጠየቅ ደርሰዋል” ሲሉ የገለጹት የቀድሞ የኢህአዴግ ባለስልጣን፣ ፓርቲው በሙስና ስም ያካሄደው የሽግግር ወቅት የማጥራት ርምጃ የፈጠረው ስሜት አሁን ድረስ እንዳለ ጠቁመዋል።

 

ሰሞኑንን ወደ አሜሪካ ያቀኑ የቀድሞ የኢህአዴግ ሰው በማግኘት ተመሳሳይ መረጃ ያሰባሰበው ዘጋቢያችን “ኢህአዴግ በከፍተኛ የመበስበስ አደጋ ውስጥ ይገኛል። በዚህም የተነሳ ካድሬው ተዥጎርጉሯል” ሲል ሪፖርት አድርጓል። ኢህአዴግ በውስጥ ያለበትን ችግር ለማድበስበስ የአባይ ግድብ ላይ ትኩረት በመስጠት “የንቅናቄ ሃይል” በማስፋፋት ላይ እንደሆነም ጠቁሟል።

 

ድፍን ህዝብ የአባይ ግድብን አስመልክቶ ያለው ስሜት በበጎ መልኩ የሚታይ በመሆኑ ኢህአዴግ ይህንኑ የህዝብ ስሜት ለቅስቀሳና ለበሽታው መደበቂያ ለማድረግ እየተጠቀመበት እንደሆነ ተጠቁሟል። የህጻናት ፕሮግራሞች ሳይቀሩ አባይ ላይ ያነጣጠሩ ቅስቀሳዎች እያስተላለፉ መሆናቸውን ያመለከቱት ሰው፣ “ስለ አባይ ግድብ የሚባለውና የሚሰራው ፕሮግራም ችግር የለውም። በአግባቡ ቢሰራበት ብሔራዊ ስሜት ሊገነባበትም በተቻለ ነበር። ይሁን እንጂ ዓለማው የችግር ማለባበሻ እንዲሆን መደረጉ ነው” ብለዋል።

 

“መለስ ኢትዮጵያን ቢወድ ኖሮ ከባድመ ጦርነት በኋላ የፈረሰውን ብሔራዊ አንድነትና መግባባት መልሶ መትከል ይቻል ነበር” በማለት የተናገሩት እኚሁ ሰው “በወቅቱ ይህንን ሃሳብ ያነሱ ሰዎች ነበሩ” ሲሉ ቁጭታቸውን ይሰነዝራሉ። በማያያዝም ኢህአዴግ የአባይን ግድብ ተንተርሶ ብሔራዊ አንድነት የሚገነባበት፣ መቀራረብና በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር ብሔራዊ መግባባት የሚደረስበት፣ ለወደፊቷ ኢትዮጵያ መሰረት የሚጣልበት ቢያደርገው እውነተኛው የኢትዮጵያ ህዳሴ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል።

 

በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝን በውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም ለመተካት ህዋሀቶች የሚያደርጉት ሽርጉድ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ሪፖርት መቅረቡ ተሰምቷል። ይኽው ሪፖርት የቀረበላቸው ክፍሎች ቀደም ሲል እንዳደረጉት የህወሃትን ከፍተኛ አመራሮች በማነጋገር ስህተት እንዳይሰሩ እየወተወቱ ነው።

 

 


መንግሥት ማኅበረ ቅዱሳንን በአክራሪነት አልፈረጅኹም አለ

$
0
0
  • sendek-miyazeya-2006እንደ ፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሕዝብ ግንኙነት ሓላፊ ገለጻ በማኅበረ ቅዱሳን ውስጥ በአክራሪነት የተፈረጁት ‹አንዳንድ ግለሰቦች›÷ ‹‹አንዲት ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት›› የሚሉቱም ናቸው፡፡ ታዲያ ምን ይበሉ?!
  • ‹‹በይፋ አክራሪ ናችኹ ያለን አካል የለም፡፡›› /ተስፋዬ ቢኾነኝ፤ የማኅ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ/
  • ‹‹በጉዳዩ ላይ የጠራ ነገር የለም፤ ነገር ግን ጢስ አለ፡፡ ከጢሱ በስተጀርባ ያለው እሳት ይኹን እሳተ ገሞራ ባይታወቅም ለጊዜው ግን ማኅበሩን በተመለከተ ግልጽ የኾነ ነገር የለም።›› /ዲ.ን ዳንኤል ክብረት/

/ሰንደቅ፤ ፱ ቁጥር ፬፻፵፰፤ ሚያዝያ ፩ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም./

ዘሪሁን ሙሉጌታ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በ፲፱፻፺፬ ዓ.ም ለሦስተኛ ጊዜ ጸድቆ በተሰጠው መተዳደርያ ደንብ መሠረት የተቋቋመውን ማኅበረ ቅዱሳንን የኢትዮጵያ መንግሥት በአክራሪነት አለመፈረጁን አስታወቀ፤ ማኅበረ ቅዱሳንም በበኩሉ በይፋ በአክራሪነት የፈረጀው አካል እንደሌለ ገልጦአል።

በፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት ሓላፊ አቶ አበበ ወርቁ እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ አቶ ተስፋዬ ቢኾነኝ÷ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳንን መንግሥት በአክራሪነት ፈርጆ ሊያፈርሰው ነው፤›› የሚለውን አስተያየት በተመለከተ ተጠይቀው እንደመለሱት፣ ማኅበሩ በአክራሪነት በይፋ መፈረጁን እንደማያውቁ ተናግረዋል።

‹‹የአክራሪነት ፍረጃው ጉዳይ ከምን አንጻር እንደተነሣ ግልጽ አይደለም። በየትኛውም መድረክ ላይ ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ነው ተብሎ የተነሣበት ኹኔታ የለም። ማኅበረ ቅዱሳንን የማሳደግ፣ የመደገፍ ሓላፊነት የራሱ የሃይማኖቱ ተቋም እንጂ የመንግሥት ጉዳይ አይደለም፤ የማፍረስ ዓላማ አለው የተባለውም ስሕተት ነው፤›› ያሉት አቶ አበበ፣ ‹‹መንግሥት ማኅበረ ቅዱሳንን ለማፍረስ ሕገ መንግሥቱም አይፈቀድለትም፤ የመንግሥትም ባሕርይ አይደለም፤›› ብለዋል።

‹‹የመንግሥት ፍላጎት ሃይማኖት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ተከትሎ በአግባቡ በዚህች ሀገር ላይ ሰላማዊ የአምልኮ ሥርዓት እንዲፈጸም እንጂ በሲኖዶሱ የተደራጀን ተቋም ሊያፈርስ የሚችልበት ሕገ መንግሥታዊ ሥልጣን የለውም፤›› ሲሉ አቶ አበበ ጨምረው ገልጸዋል።

‹‹መንግሥት ማኅበረ ቅዱሳንን ሊያፈርስ ነው፤›› የሚለው ጉዳይ የተለያየ መነሻ እንደሚኖረው የጠቀሱት የሕዝብ ግንኙነት ሓላፊው፣ ጉዳዩ ከግንዛቤ እጥረት ወይም ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ የአክራሪነት አስተሳሰብን የማስፋፋት ፍላጎት ባላቸው አካላት የተነሣ ሊኾን እንደሚችል ገምተዋል።

‹‹ሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሃይማኖትን ሽፋን አድርጎ የሚካሔድን እንቅስቃሴ ሊሸከም የሚችል ትከሻ እንደሌለው በተደጋጋሚ አሳይቷል፤ ትልቅ ትግልም አካሒዷል፤›› ያሉት አቶ አበበ፣ የአሉባልታው ምንጭ አክራሪነትን በማስፈንና አክራሪነትን በመዋጋት መካከል ባለው ፍልሚያ የተቀሰቀሰ አሉባልታ ነው ብለዋል።

‹‹ጉዳዩ በሬ ወለደ ነው፤›› የሚሉት ሕዝብ ግንኙነቱ፤ ‹‹ከዚኹ አካባቢ[ከማኅበረ ቅዱሳን] አክራሪነትን ሊደግፉ የሚችሉ ግለሰቦች ሊኖሩ ይችላሉ፤›› ብለዋል። ‹‹የሰላማዊው አምልኮ ሥርዓት እየጠነከረ በሄደ ቁጥር የአክራሪው መድረክ እየጠበበ ስለሚመጣ ከሕዝብ ልንነጠል ነው በሚል ፍራቻ ልክ በሕዝበ-ሙስሊሙ አካባቢ የሐሰት ወሬ ተዘርቶ መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ ገብቷል እንዳሉት ኹሉ አሁን ደግሞ ወደ ሕዝበ-ክርስቲያኑ በማሰራጨት በባዶ ጩኸት ሕዝቡን ለማሳሳት የታለመ ነው፤›› ብለዋል።

‹‹መንግሥት ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ምንም ዓይነት ስጋት የለውም፤›› ያሉት አቶ አበበ፣ ማኅበረ ቅዱሳን ከመንፈሳዊ ሥራው ጎን ለጎን እያካሄደ ያለው የልማት፣ የሰላም፣ የዴሞክራሲ ሥራ ስለሚሠራ፣ መንግሥት ከያዘው አጀንዳ ጋር ስለሚጣጣም በአጋዥነት ስለሚያየው ይደግፈዋል እንጂ አያፈርሰውም ብለዋል። ይህ ሲባል ግን እንደ ማንኛውም ተቋም የተቀደሰውን ዓላማ የሚያራክሱ፣ ማኅበሩን ወዳልኾነ አቅጣጫ የሚወስዱ ግለሰቦች አይኖሩም ማለት እንዳልኾነ ጠቅሰዋል። በተለይም ‹‹አንድ ሃይማኖት! አንድ ሀገር! አንድ ጥምቀት!›› እያሉ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ሊኖሩ ይችላሉ። እንደዚህ ዓይነቶቹ ግለሰቦች በአክራሪነት ሊፈረጁ ይችላሉ ብለዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ አቶ ተስፋዬ ቢኾነኝ ስለ ጉዳዩ ተጠይቀው፣ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና አግኝቶ መተዳደርያ ደንብ ተቀርፆለት የሚተዳደር ማኅበር እንደኾነ አስታውሰው፤ ማኅበሩ በቤተ ክርስቲያኗ ሥር የሚያገለግል ማኅበር በመኾኑ ከአክራሪነት ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም፤›› ብለዋል።

‹‹ክርስትናችን አክራሪነትን የሚያስተምር አይደለም። የማኅበሩም አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ከአክራሪነት ጋር ምንም የሚያገናኝ ሥራ የለውም። የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እየሰጠ ያለ ማኅበር ነው፤ በጉዳዩም ላይ በይፋ የደረሰን የተጻፈ፣ በቃልም የተባልነው ነገር የለም። ካለም ልንወያይ፣ አስፈላጊውን ነገር ልንተባበር እንችላለን፤›› ሲሉ አቶ ተስፋዬ ከአክራሪነት ፍረጃ ጋር በተያያዘ በይፋ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ተናግረዋል፤ ማኅበሩም የተለመደ አገልግሎቱን እየሰጠ እንደሚገኝም ጨምረው ገልጸዋል።

ማኅበሩን በተመለከተ እየተነሣ ያለው የፍረጃ ሐሳብ ምንጩ ምን እንደኾነ አናውቅም ያሉት አቶ ተስፋዬ፣ ምንጩን ሊያውቁ ይችላሉ ብለን የምንገምተው ሚዲያዎቹ ናቸው። እኛ ምንም የምናውቀው ነገር የለም። እንደማንኛውም ጉዳዩን እንደሚከታተል አካል ነው የምናየው ብለዋል።

ከዚህ ቀደም ከአክራሪነት ጋር በተያያዘ በወጡ ሰነዶች ላይ ማኅበሩ መጠቀሱን በተመለከተ አቶ ተስፋዬ ተጠይቀው፣ በማኅበር ደረጃ በይፋ በግልጽ የተጠቀሰ ነገር እንደሌለ ተናግረዋል። ማኅበሩን በቀጥታ የሚመለከት በደብዳቤም ኾነ በሌላ መንገድ የተባለ ነገር የለም ብለዋል።

ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

አንዳንድ የማኅበሩ ምንጮች በመጋቢት ፳፻፭ ዓ.ም. ‹‹የፀረ አክራሪነት ትግል የወቅቱ ኹኔታና ቀጣይ አቅጣጫዎች››*በሚል ርእስ በተዘጋጀ ሰነድ ላይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና መድረክ የአክራሪነት አደጋ ያለው በሃይማኖት ሽፋን በሚንቀሳቀሱና የከሰሩ ፖሊቲከኞች ምሽግ በመኾን ያገለግላሉ በተባሉ ማኅበራት ውስጥ ነው መባሉ፤ በቅርቡም በሐዋሳ ከተማ‹‹አክራሪነትና ጽንፈኝነት ችግሮቹና መፍትሔዎቹ››**በሚል ርእስ በቀረበ ጽሑፍ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የአክራሪዎች ምሽግ የኾኑት የወጣት ማኅበራት አደረጃጀቶች መኾናቸውንና እኒህም ማኅበራት በሃይማኖት ተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ይኹንታ ያላቸው ከመኾኑም በላይ ማኅበራቱ ከጽንፈኛ የፖለቲካ ኃይሎች ጋራ ግንኙነት እንዳላቸው መጠቀሱእንዲሁም ከፓትርያርክ ምርጫው፣ ከቀድሞ ፓትርያርክ ጋር ዕርቅ ለመፍጠር የተደረገውን ጥረት ማኅበሩን ከከሰሩ ፖለቲከኞች ጋር ለማስተሳሰር መሞከሩና ሌሎችም ተያያዥ ጉዳዮች የማኅበሩ አባላት መንግሥትን በጥርጣሬ እንዲያዩት መደረጉን ይገልጻሉ።

በማኅበረ ቅዱሳን ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ከነበራቸው አመራሮች አንዱ የነበሩት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በግል ስለ ኹኔታው ተጠይቀው፣በጉዳዩ ላይ የጠራ ነገር አለመኖሩን፣ ነገር ግን ጢስ መኖሩን ገልጸዋል። ከጢሱ በስተጀርባ ያለው እሳት ይኹን እሳተ ገሞራ ባይታወቅም፤ ለጊዜው ግን ማኅበሩን በተመለከተ ግልጽ የኾነ ነገር የለም ብለዋል።

በግላቸው መንግሥት ማኅበረ ቅዱሳንን በማፍረስ ስሕተት ይሠራል ብለው እንደማይገምቱና ምናልባትም ለማኅበሩ ያሰቡ ሰዎች መስለው ለማኅበሩ የተሳሳተ መረጃ ያቀበሉ እንዲሁም በመንግሥት በኩል ማኅበሩን በተመለከተ አፍራሽ አቋም ሊያንጸባርቁ የሚችሉ አንዳንድ ግለሰብ ባለሥልጣናት ሊኖሩ እንደሚችሉ ያላቸውን ጥርጣሬ ተናግረዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን በ፲፱፻፹፬ ዓ.ም በዋናነት በእምነቱ ተከታዮች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የተመሠረተ ሲኾን፤ የአባልነት መዋጮ በመክፈልና ከፍተኛ አገልግሎት በማበርከት ተሳትፎ ያላቸው ከ፴ ሺሕ በላይ አባላትና ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ተባባሪ አባላት አሉት፤ ማኅበሩ በስብከተ ወንጌል ረገድ ከሚያከናውነው ዓበይት መንፈሳዊ አገልግሎት ባሻገር ገዳማትና የገጠር አብያተ ክርቲስያናት በልማት ራሳቸውን እንዲችሉ፣ የአብነት ት/ቤቶች እንዲጠናከሩና እንዲጎለብቱ ትኩረት ሰጥቶ በመሥራት ላይ የሚገኝ ማኅበር ነው።

>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>> 

በኦርቶዶክስ ክርስትና ሃይማኖት ሽፋን የሚንቀሳቀሱ ማኅበራት የአክራሪነትና የከሰሩ ፖሊቲከኞች ምሽግ በመኾን መገልገል ከጀመሩ ውሎ አድሯል፡፡ ከ፮ው ፓትርያርክ ምርጫ ጋራ በማያያዝ የየራሳቸው ፍላጎት የሚያሳኩ ውሳኔዎችን ለማስተላለፍና አሜሪካ ከሚገኘው ስደተኛው ሲኖዶስ ከሚባለው ቡድን ጋራ የዕርቅ ኹኔታ በሚል እንቅስቃሴዎችን ያደርጋሉ፡፡

በዚኽ በራሳቸው በፈጠሩት ትርምስ ውስጥ መንግሥት እጁን አስገብቷል ወዘተ እያሉ የኦርቶዶክስ አማኞችን ለማወናበድ ይሞክራሉ፡፡ በራሳችንም እንደሌላው ኃይል ሰልፍ ልንወጣ ይገባል በሚል የዐመፅና የሁከት ቅስቀሳ ለማድረግ ይፈልጋሉ፡፡

በተለይም ሰሜን አሜሪካ የሚገኘው ራሱን ስደተኛው ሲኖዶስ ብሎ የሚጠራው አካል ሰላማዊ፣ አሳታፊና ግልጽ ኾኖ የተካሔደውን የ፮ው ፓትርያርክ ምርጫ አውግዘናል በማለት መግለጫ ሲሰጥ የሰነበተ ቢኾንም የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዩ ሕዝብ ጆሮውን ሳይሰጠው አልፏል፡፡ በሒደትም ይህ ኃይል ሰላም እንዳልኾነ፣ የሰላም ጥረቶችን በሙሉ ሲያሰናክል የሰነበተ፣ ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴ ሳይኾን የከሰሩ ፖሊቲከኞች እንቅስቃሴ መኾኑን ግንዛቤ ይዟል፡፡

በማኅበረ ቅዱሳን ውስጥ የመሸጉ የትምክህት ኃይሎች ጽንፈኛ የፖሊቲካ ኃይሎች አካል በመኾን በጋዜጣና በመጽሔት ሕዝባችንን ለዐመፅና ሁከት ለማነሣሣት ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡ በስደተኛው ሲኖዶስ በመሸፈንም እያንዳንዱ ሌላ ቀን ኢትዮጵያ የምትባል አገር የሌለች አስመስለው የግንቦት ሰባትን ከበሮ ሲመቱ ከርመዋል፡፡ (የፀረ አክራሪነት ትግል የወቅቱ ኹኔታና ቀጣይ አቅጣጫዎች፤ መጋቢት ፳፻፭ ዓ.ም.)

**slide presentation by Dr. Shiferaw000

የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ቀዳሚ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ሆነ

$
0
0

ሚያዚያ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያ በ2005 በጀት ዓመት ከኤክስፖርት ካገኘችው ገቢ ይበልጥ በውጪ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊን በሐዋላ መልክ ያገኘችው ገቢ እንደሚበልጥ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተገኘ የጹሑፍ መረጃ አመልክቷል።

መረጃው እንደሚያሳየው በ2005 በጀት ዓመት አገሪቱ ከኤክስፖርት 3.1 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ያገኘች ሲሆን ኢትዮጵያውያን ከውጭ ከሚልኩት ገንዘብ ደግሞ 3 ቢሊዮን 9 መቶ ሚሊዮን ዶላር አግኝታለች፡፡ በ2004 በጀት ዓመትም ከሐዋላ እና ከኤክስፖርት ያገኘቸው ገቢ ተመሳሳይ ማለትም እያንዳንዳቸው 3.2 ቢሊየን ዶላር መሆኑን መረጃው ያሳያል፡፡

መረጃው የሐዋላ ገንዘብ በፍጥነት እያደገ ሲመጣ በአንጻሩ አገሪቱ እንደቡና ፣የቅባት እህሎችና ጥራጥሬና የመሣሠሉትን በመላክ የምታገኘው ዓመታዊ ገቢ እያሽቆለቆለ መምጣቱን ያሳያል፡፡

ESAT Radio Tuesday November 19, 2013የኤክስፖርት ዘርፍ ባለፉት ሶስት ዓመታት መንግስት ከያዘው እድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አንጻር አፈጻጸሙ ደካማ መሆኑን መረጃው የሚጠቁም ሲሆን ከገቢ ንግድ ጋር ያለው የንግድ ሚዛን ጉድለት እየሰፋ መምጣቱ አሳሳቢ መሆኑን ያመለክታል፡፡በ2004 የገቢ ንግድ(ኢምፖርት) መጠን 11 ቢሊየን ዶላር ሲሆን በ2005 ዓ.ም ወደ 11. ቢሊዮን 500 ሚሊዮን ዶላር ከፍ ብሎአል፡፡ የሸቀጦች የወጪ ንግድ ገቢ ከሸቀጦች የገቢ ንግድ ወጪ ጋር ሲነጻጸር በሚጠበቀው ደረጃ ዕድገት ባላማሳየቱ የንግድ ሚዛን ጉድለቱ በ2003 ዓ.ም ከነበረበት 5 ቢሊዮን 500 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በ2005 ዓ.ም ወደ 8. ቢሊየን 400 ሚሊዮን ዶላር እንዲሰፋ ማድረጉን መረጃው ጠቁሟል፡፡ ይህን የንግድ ሚዛን ጉድለት ለማጥበብ መፍትሔው ኤክስፖርትን ማሳደግ ነውም ብሏል፡፡

እጅግ የተለጠጠ ነው በሚል ትችት የሚቀርብበት የመንግስት የአምስት ዓመቱ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለማሳካት ታሳቢ ከተደረገው ገንዘብ መካከል ብድርና እርዳታ አንዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡ መረጃው እንደሚያሳየው ከዓለም አቀፍ ተቋማትና ለጋሽ መንግስታት አገሪቱ ያገኘችው ዕርዳታ በ2005 ዓ.ም ማሽቆልቆል አሳይቷል፡፡

በ2004 በጀት ዓመት 1 ቢሊዮን 800 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ዕርዳታ የተገኘ ሲሆን በ2005 ዓ.ም ወደ 1.ቢሊዮን 300 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ ብሏል፡፡ ይህም የተጀመሩ ፕሮጀክቶች ላይ የራሱ የሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ተገምቷል፡፡

Source: Ethsat

“ንብረት የማፍራት መብት መገለፅ ያለበት በብሔረሰብ ደረጃ ሳይሆን በግለሰብ ነው” (አቶ ተክሌ በቀለ)

$
0
0

አቶ ተክሌ በቀለ (የአንድነት ፓርቲ ም/ፕሬዝዳንት)

በዘሪሁን ሙሉጌታ

 

አቶ ተክሌ በቀለ (የአንድነት ፓርቲ ም/ፕሬዝዳንት)

አቶ ተክሌ በቀለ (የአንድነት ፓርቲ ም/ፕሬዝዳንት)

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሁለተኛውን የሕዝብ ንቅናቄ መጀመሩ የሚታወስ ነው። ፓርቲው ከዚህ ቀደመ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል የሕዝባዊ ንቅናቄ መድረኮች አዘጋጅቷል። አሁን ደግሞ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪ ቃል ፕሮግራሙን ይፋ አድርጓል። ባለፈው እሁድ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም በደሴ ከተማ ፕሮግራሙን በሰላማዊ ሰልፍ አከናውኗል።

በደሴ ስለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍና “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚለው ርዕሰ ጉዳይ ላይ የፓርቲውን ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ተክሌ በቀለ፣ የፓርቲው የውጪ ግንኙነት ኃላፊ ኢንጂነር ዘለቀ ረዲ እና የፖርቲው ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ሰልፉን መርተውታል። ከመሬት ባለቤትነትና ከሰልፉ ጋር በተያያዘ የፓርቲውን ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ተክሌ በቀለን አነጋግረናቸዋል።

ሰንደቅ፡- በደሴ ያካሄዳችሁት ሰላማዊ ሰልፍ ምን ያህል የተሳካ ነበር?

አቶ ተክሌ፡- መጀመሪያ ፕሮግራሙን ያሰብነው በሐዋሳ፣ በአዲስ አበባና በደሴ ከተሞች ነበር። እንደአጋጣሚ ሆኖ የደሴው በመሳካቱ ቅስቀሳ ስናደርግ ቆይተን ሰልፉን ለማካሄድ በቅተናል። የአዲስ አበባውና የሐዋሳው ለሌላ ጊዜ ተዛውሯል። የሐዋሳውን በራሳችን ምክንያት ያራዘምነው ሲሆን፤ የአዲስ አበባው ግን በአስተዳደሩ ችግር ምክንያት ነው።

የደሴው ሰላማዊ ሰልፍ እንደጠበቅነው በከፍተኛ ሞቅታ ነው ፕሮግራሙ የተጀመረው። በርካታ ሕዝብ ተገኝቶልናል። የሰልፉ አካል ሆኖ በመሐል መንገድ ላይ መፈክር እያሰማ ሲሄድ የነበረው የሕዝብ ብዛት ከ50 እስከ 60 ሺህ ገምተነዋል። ከሰልፉ ጎን ለጎን ዳርና ዳር የሚሄደው ሕዝብ በግምት መቶሺህ ይሆናል። በእኛ እምነት ሕዝቡ በመሬት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የመሬት ጉዳይ የሚያስከፍላቸውን ማኅበራዊ ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በመገንዘብ ከፍተኛ የሆነ መነሳሳት አሳይቷል። በተደረገው የሁለት ቀን ቅስቀሳ ያን ያክል ሕዝብ መውጣቱ የሕዝቡም ስሜት ከፍተኛ እንደነበር ያሳያል። በዚህ ወቅት እኔን ያስታወሰኝ በ2002ቱ መርጫ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ “ደሴም ሳይቀር አሸንፈናል” ብለው ነበር። አሁን ሳየው ግን የኢህአዴግ የምርጫ ኮንትራት ሳያበቃ ይሄን ያክል ሕዝብ ወጥቶ “በቃኝ” የማለቱ ሁኔታ ሲታየ ምርጫውን እንዴት ነበር ያሸነፉት ብዬ እንዳስብ አድርጎኛል።

ሰንደቅ፡- መሬት የፖሊሲ ጉዳይ እንደመሆኑ መጠን ከሰላማዊ ሰልፍ ይልቅ በሕዝባዊ ውይይት ማካሄዱ ይሻላል፤ አለበለዚያ በትንሹም በትልቁም ሰላማዊ ሰልፍ መጥራት የፓርቲውን ደጋፊዎች ያሰለቻል የሚል ነገር እየተነሳ ነው። ለዚህ ኀሳብ ያለዎት ምላሽ ምንድነው?

አቶ ተክሌ፡-ፕሮግራሙ ሲጀመር የመረጥናቸው ከተሞች ነበሩ። አዲስ አበባን ጨምሮ በርካታ የሀገሪቱ ምሁራን የሚገኙበት የአዳራሽ ውስጥ ስብሰባ አቅደን ነበር። ወደ አደባባይ እየገፋን ያለው ኢህአዴግ ነው። መሬትና ከመሬት ጋር ተያይዞ ለሚፈጠሩ ማኅበራዊ ኢኮኖሚያዊና የፍትህ ችግሮች በተመለከተ በሰላማዊ ሰልፍና በሕዝባዊ የአዳራሽ ስብሰባ ለይተን ነበር። ነገር ግን ገና ከመጀመሪያው አዲስ አበባ ላይ አዳራሽ ማግኘት ተቸግረናል። የመንግስት አዳራሾች ብቻም ሳይሆን በገንዘባችን ከፍለን የሆቴሎችን አዳራሽ ማግኘት አልቻልንም። ወደ ጎዳና እየገፋን ያለው ገዢው መደብ ነው።

ሰንደቅ፡- የመሬት ችግር በከተማና በገጠርም የተለያየ ነው። በሀገሪቱም የችግሩ አይነትና መጠንም የተለያየ ነው። በቀላሉ የሕዝብ ድጋፍ አላችሁ ተብሎ በሚገመተው ደሴ ከተማ ከማካሄድ ይልቅ በደቡብና ኦሮምያ ክልሎች ለምን እንቅስቃሴውን አልጀመራችሁም?

አቶ ተክሌ፡- በአጠቃላይ በመሬት ላይ ያለን እይታ ሦስት አይነት ነው። መሬት በግል፣ በወል ወይም በመንግስት ስር መሆን አለበት የሚል የመሬት ስሪት አቋም አለን። ኢህአዴግ ደግሞ መሬትን በተመለከተ የሚያስቀምጠው ከእኛ ፍፁም የተለየ ነው። በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 40 ንዑስ ቁጥር ስድስት ላይ መሬት የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንደሆነ አድርጎ ነው የሚያስቀምጠው። ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በባህል፣ ወዘተ እንጂ ንብረት በማፍራት መብታቸው ሊገለፅ አይችልም። ንብረት የማፍራት መሠረታዊ መብት መገለፅ ያለበት በብሔረሰብ ደረጃ ሳይሆን በግለሰብ ነው። ኢህአዴግ ብሔር ብሔረሰቦች የሚያቋቁሙት መንግስት ነው ብሎ ስለሚያምን በተዘዋዋሪ መሬት የመንግስት እንደሆነ መረዳት ይቻላል። ይህ ማለት ደግሞ በብሔር ብሔረሰቦች ስም መሬትን ወይም የሕዝብን ንብረት ጠቅልሎ ኢህአዴግ ወስዶታል ማለት እንችላለን። በሌላ አነጋገር ግለሰቦች ከመሬት ባለቤትነት ውጪ ሆነዋል ማለት ነው። በእኛ እምነት የከተማ መሬት የግለሰቦች መሆን አለበት ብለን እናምናለን። የገጠሩ ደግሞ አስቀድሜ እንደነገርኩህ በግል፣ በወል ወይም በጋራ እና በመንግስት መያዝ አለበት።

ወደ ጥያቄህ ስመጣ አጠቃላይ የኢህአዴግ የመሬት ፖሊሲ በብሔር ብሔረሰቦች ሽፋን ከመውሰዱ አንፃር ችግሩ የመላ ሀገሪቱ ነው። ስለዚህ በደሴም ጀመርከው በደቡብ ችግሩ አንድና ተመሳሳይ ነው። በእርግጥ በደሴ የጀመርነው የተሻለ ተቀባይነት አለን በሚል መነሻ ብቻ አይደለም። አንድነት አጠቃላይ ሕዝቡ ከተቃዋሚው ጎራ ጋር እንደወገነ እንረዳለን። ኢህአዴግ የሚዘጋብን ሕዝቡ እንደሚደግፈን ስለሚያውቅ ነው። በእርግጥ አንድነት ያልደረሰባቸው፣ ሌሎች ተቃዋሚዎች ጠንካራ ስራ የሚሰሩባቸው ቦታዎች ይኖራሉ። ያም ሆኖ ስንጀምረው አዲስ አበባና ሐዋሳ ነበር። ደሴ አልነበረም።

ሰንደቅ፡- ገዢው ፓርቲ ተቃዋሚዎች በመሬትም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ላይ የጠራ ፖሊሲ የላቸውም እያለ ነው። በእናንተ እምነት በአሁኑ ወቅት የጠራ ፖሊሲ አለን ብላችሁ ታስባላችሁ?

አቶ ተክሌ፡- በመሬት ላይ ብቻ አይደለም። በአጠቃላይ ከመሬት ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች በርካታ ናቸው። የሀገሪቱ አንጡራ ሀብት መሬት እንደሆነ አንረዳለን። ዋነኛ ትኩረታችንም የመሬት ምርታማነት፣ ባለቤትነትና ልማት ነው። ከገዢው ፓርቲ ጋር ካሉን የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብት የአከባበር ልዩነቶች ባሻገርም አንዱና ዋነኛው መሬት ነው። ከሀገሪቱ የችግር ምንጮች ውስጥ አንዱ የመሬት ባለቤትነት ነው። ስለዚህ በዚህ ዙርያ ያሉ ችግሮችን ተረድተናል። ችግሮቹን በመረዳታችንም የጠራ ፖሊሲ ቀርፀናል። ከመሬት ባሻገርም በፋይናንስም በለው፣ በግብርናም ሆነ በውጪ ጉዳይ በማኅበራዊ ጉዳዮች ሀገሪቷዋን ከድህነትና ኋላቀርነት ያወጣል ብለን እናምናለን። ችግራችን የቀረፅናቸውን አማራጭ ፖሊሲዎች ለሕዝብ ማድረስ የምንችልበት የሚዲያ እና ወደ ሕዝቡ የምንቀርብበት መድረክ መዘጋቱ ነው። እና ኢህአዴግ “ተቃዋሚዎች አማራጭ የላቸውም” የሚለው አባባል ድሮ የቀረ ተረት ተረት ነው።

ሰንደቅ፡- በተቃዋሚዎች በኩል ወጥ የሆነ የመሬት ፖሊሲ አይስተዋልም። በተለይ በኦሮሞ ብሔር የተደራጁ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መሬት የመንግስት ይሁን የሚል ዝንባሌ አላቸው። ሌሎቻችሁ ደግሞ “መሬት ይሸጥ ይለወጥ” እስከማለት ትደርሳላችሁ ይህ ደግሞ በምርጫ ወቅት አያስቸግርም?

አቶ ተክሌ፡- ተመሳሳይ ፕሮግራም ያላቸው ፓርቲዎች ውህደት ፈጥረው በአንድ ላይ ቢንቀሳቀሱ ችግሩ ሊፈታ ይችላል። የግል ስልጣንና የቡድናዊ ጥቅምን አስወግደው ወደ ውህደት ቢመጡ መልካም ነው። አሁን ፓርቲዎች ሚዛን በማይደፉ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ ቢሆንም፤ ያነገቡት ፕሮግራም የተለያየ አይደለም፤ በመሆኑም ሕዝቡ የተለያዩ ፓርቲዎችን ቢመርጥም የሚመረጠው ፕሮግራም ግን ተቀራራቢና በአመዛኙ አንድ አይነት ነው ለማለት ያስደፍራል። በእርግጥ ከመድረክ ጋር በተያያዘ አንዱ ልዩነት የመሬት ባለቤትነት ጉዳይ ነው። ሆኖም ግን በመለስተኛ ፕሮግራማችን ላይ መሬትና ያልተፈቱ ሌሎች ጥያቄዎችን ሕዝቡ እንዲፈታቸው ተስማምተናል። ነገር ግን ሕዝቡ ደግሞ ደሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶቹን ሙሉ በሙሉ አልተጎናፀፈም። መሠረታዊ ዴሞክራሲያዊ መብቶቹን ያልተጎናፀፈ፣ ሕዝብ ዋነኛ በሆኑ የሕዝብ ችግሮች ላይ መፍትሄ ለማምጣት መጀመሪያ የተነፈገውን መብት ማግኘት አለበት የሚል መረዳት አለ። በመሠረቱ የተጠቀሱት የኦሮሞ ድርጅቶችም መሬት የመንግስት ይሁን ሳይሆን፤ ሕዝቡ ይወስን እያሉ ነው። አረናን ብትወስደው መሬት የግል ቢሆንም፤ መሸጥ መለወጥ የለበትም ይል እና ጉዳዩ የሕገ-መንግስት ማሻሻያን የሚጠይቅ እንደመሆኑ ሕዝቡን ቀጥተኛ ተሳትፎ የሚጠይቅ ነው። በድምሩ ስታየው መሬትን በተመለከተ በተቃዋሚዎች ካምፕ ያለው መረዳት የሚያራራቅ ሳይሆን ሊታረቅ የሚችል ጉዳይ ነው።

ሰንደቅ፡- ፓርቲያችሁ በአሁኑ ወቅት የመሬትን ጉዳይ ያነሳው ለምንድን ነው?

አቶ ተክሌ፡- ኢትዮጵያ ውስጥ የስልጣን መባለግን ጨምሮ ከፍተኛ የሙስና ምንጭ የሆነው መሬት ነው። የመሬት ጉዳይ የፍትህ እጦትና የመልካም አስተዳደር ችግር መገለጫዎች አንዱና ዋነኛው ነው። ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ አዝጋሚነትና ለማኅበራዊ ችግሮች ምንጩ የመሬት ባለቤትነትና የይዞታ አስተዳደር ችግር ነው። ይህንን እኛ ብቻ ሳንሆን እራሱ ገዢው ፓርቲ የሚያምንበት ጉዳይ ነው። በዚህ ወቅትም ጉዳዩን ልናነሳው የቻልነው ከመሬት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮች ላይ ግንዛቤ ለመጨበጥ፣ ባለን ፖሊሲም ላይ እንደ ግብአት የሚያስፈልግ ነገር ካለም ለማካተት ነው። በዋናነት ግን የሀገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ቀውሶች መገለጫ መሆኑን፣ የኢህአዴግ የመሬት ፖሊሲ የተሳሳተና ያስከተለውንም በሙስና የመጨማለቅ ሁኔታን ለማሳየት ነው።

በአሁኑ ወቅት መሬት በኢንቨስትመንት ስም የሙስና መንጭ ሆኗል። ግለሰብ በግለሰብነቱ ከመሬት ባለቤትነት ከራቀ በፖለቲካ ዓይን ስታየው የካድሬዎች መጫወቻ ይሆናል። ይህንን ማረጋገጥ የሚቻለው በተለያዩ ጊዜአት መንግስት የሚያስራቸው ባለስልጣናቱን እያየን ነው።

ሰንደቅ፡- በቀጣይ የምታካሂዱት እንቅስቃሴስ ምን ይመስላል?

አቶ ተክሌ፡- በትላልቅ ከተሞች በተለይም ምሁራንን በቀላሉ በምናገኝበት ቦታ የአዳራሽ ስብሰባዎች እያደረግን፣ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ይደረጋል። በገጠር ደግሞ በወረዳ ደረጃ የሚሰሩ ስራዎች አሉ። ሰላማዊ ሰልፎቹም በተመረጡ ከተሞች ይቀጥላሉ። እንደነገርኩህ መሬትን በተመለከተ ሕዝቡ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኝ ዋነኛ ዓላማችን ነው። በገጠሩም በከተማም ሰፊ እንቅስቃሴ እናደርጋለን ብለን አቅደናል።

ሰንደቅ፡- ይህ መሬትን ማዕከል ያደረገ እንቅስቃሴ በቀጥታ ከ2007ቱ ምርጫ ጋር የሚያያይዘው ነገር አለ?

አቶ ተክሌ፡- ከምርጫ ጋር አይያያዝም። ምርጫ እንገባለን ወይስ አንገባም የሚለው የብሔራዊ ምክር ቤቱ ውሳኔ ነው የሚሆነው። በአጠቃላይ ያሉትን ሁኔታዎች እያየን የምንወስነው ጉዳይ ነው። አሁን ግን የመሬት ጉዳይ ያለንን ፖሊሲ ከማዳበርና ኅብረተሰቡም በመሬት ላይ የጠራ

የአሩሲና አካባቢው ተወላጅ አማሮች አስቸኯይ መልእክት ለኢትዮጲያዊው!!!

$
0
0

የአሩሲና አካባቢው ተወላጅ አማሮች አስቸኯይ መልእክት ለኢትዮጲያዊው!!! (መጋቢት 30፣ 2006 ዓ.ም.)

454በአማራው አናት ላይ እያንዣበበ ያለውን የጅምላ እልቂት እንዴት ወገኖች ከመጤፍ እንዳልቆጠራችሁት ለኔ ትልቅ እንቆቅልሽ ነው የሆነብኝ። መቼም ኢትዮጲያዊያኖች ትልቅ የግንዛቤ ችግር ነው ያለብን። ከሰሞኑ በአሩሲ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች በተገኙበት የተመረቀው በተቆረጠ እጅ ላይ የተቀመጠ ጡት የሚያሳይ ሀውልት ከፍተኛና ምናልባትም በኛ ትውልድ ያልተስተዋለ ጎሳን መሠረት ላደረገ ፍጅት ብዙ እርምጃዎችን ያንደረደረን ድርጊት መሆኑን ምን ያህላችን ያስተዋልነው ጉዳይ እንደሆነ ሳሰላስለው ብዙዎቻችን እያስገመገመ ያለውን አርማጌደን አይቀሬነት አምነን የተቀበልን ያህል እንዲሰማኝ ሆኗል። በምረቃው ቦታ የመገኘት እድል የገጠማቸው የአካባቢው ተወላጅ አማሮች በስነስርዓቱ ላይ ስለተገኘው ግዙፍ መጠን የነበረው ታዳሚ እንዲህ ላለ ታላቅ ጥፋት መሳሪያ መሆን ታሪክ የማይረሳው እጅግ አሳዛኝና አሳፋሪ ድርጊት መሆኑን ገልፀው አሳሳቢም ነው ብለዋል።

ታዳሚው ፊት ላይ ይነበብ የነበረውም የጥላቻ ውፍረትና የበቀልተኝነት ስሜት ስለተከታዩ ነገር አመላካች መሆኑን በሀዘን ገልፀዋል። እስከ አሁን ድረስም በኦነግ እና ኦህዴድ ጭፍን ብሄርተኛ ተከታዮች ዘንድ ሲሰበክ የነበረውን የአማራ ጎሳን ከኦሮሚያ የማፅዳት ውጥን የይለፍ ምልክት የሰጠ ድርጊት አድርገን እንቆጥረዋለን ብለዋል። አክለውም ሁኔታውን ተከትሎ ሀውልቱ በቆመበት አሩሲና አካባቢው እየተስተዋለ ያለው አንዳንድ አፍራሽ እንቅስቃሴ ይህን እምነታቸውን ምክንያታዊ እንደሚያደርገው ገልፀዋል። የዚህ ሴራ አንዱና ብቸኛው አላማ አማራውን ማስፈጀት መሆኑን ገልፀው ሀውልቱም ለዚህ በአማረው ላይ ለሚፈፀመው የዘር ማጥፋት ህያው ማስጠየቂያ እንደሆነ አብራርተዋል። በህዝቡ መካከል ያለመቻቻልና የጥላቻ መንፈስ ስለሌለ እንዲቀሰቀስ የታሰበው የጎሳ ግጭት የመነሳት እድሉ ጠባብ ነው የሚለው የፖለቲከኞች አስተያየት የግል የፖለቲካ አጀንዳን ለመግፋት ሲባል በዜጎች ህይወት ላይ ቁማር መጫወት መሆኑን ገልፀው የፓለቲከኞቹን በንቃት እንሳተፍበታለን ስለሚሉት የሀገሪቱ ፖለቲካና በህዝቦች ተቻችሎ እና ተሳስቦ የመኖር በሀል ላይ ስላሳረፈው አፍራሽ ተፅዕኖ ያላቸውን ዝቅተኛ መረዳትም የሚያሳጣ ነው ብለዋል። ዛሬ ይህን ከአማራ የፀዳ ኦሮሚያን ስለመመስረት የሚያቀነቅኑ እንደ ኦነግ እና ኦህዴድ ያሉ ብሄርተኛ ድርጅቶች ተከታዮች የሆኑ፣ በዚህ አውዳሚ ፍልስፍና የሰከሩና ህሊናቸው የታወረ ፤ ከዚህ በፊት በአርባጉጉ በበደኖ ወዘተ የተፈፀመውን ዘግናኝ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት አይነት ለመፈፀም ወደሗላ የማይሉ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ አክራሪ ብሄርተኞች መፈልፈላቸውን በማመላከት የዚህን የእልቂት ጥንስስ አውዳሚ መጨረሻ የተቀረው ኢትዮጲያዊ ተረድቶ በሰላማዊ ሰልፍና በመሳሰሉት የእሪታ ድምፁን በአስቸኯይ እንዲያሰማላቸው ጠይቀዋል። ካራ ተስሎብን ወደ ምታችን የምንነዳ በሚሊዮን የምንቆጠር ዜጎች ፖለቲካው ውስጥ በሚርመሠመሡ ጉዶች ጉዳያችን እንዲህ አትኩሮት መነፈጉ የጉዳዩ ብቻ ሳይሆን የመፍትሄውም ብቸኛ ባለቤቶች የመሆናችንን መሪር ሀቅ የጋተን አጋጣሚ ሆኖ አግኝተነዋል ብለዋል። አያይዘውም ኢትዮጲያዊው ወገን ለጥያቄያቸው ባፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት የማይችል ከሆነ ግን እነሱ የሚቻላቸውን እንደሚያደርጉና አካባቢውን በጅምላ ከመልቀቅ ጀምሮ የተቀረው የአማራ ተወላጅም አካባቢውን በመልቀቅ የራሱንና የልጆቹን ህይወት እንዲታደግ ሰፊ ቅስቀሳ ውስጥ እንደሚሰማሩም አሳስበዋል።

አምደፂዮን ዘተጉለት፤ ከአሩሲ ነገሌ

 

የገመና ድራማው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ የፍርድ ቤት ማዘዣ ደረሰው (ማዘዣውን ይዘናል)

$
0
0

Daniel tegegne(ዘ-ሐበሻ) በከሳሽ የፊልም አሰሪ ወ/ሮ ቤተልሄም አበበ እና በተከሳሽ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ይተላለፍ በነበረው ገመና ድራማ የዶ/ር ምስክርን ገፀ ባህርይ ወክሎ የተወነውና በተለያዩ ፊልሞች ላይ የተወነው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ መካከል ያለው የፍርድ ሂደት መታየቱን ቀጥሎ አርቲስቱ የፍርድ ቤት ማዘዣ እንደደረሰው ለዘ-ሐበሻ እስከነ ማስረጃው የደረሰው መረጃ አመለከተ።

ከዚህ በፊት በዚሁ ክስ የተነሳ በካራማራ አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ የተለቀቀው አርቲስት ዳንኤል በወ/ሮ ቤተልሄም የቀረበበት አቤቱታ ለፊልም ሥራ 662 ሺህ 120 ብር ከተቀበለ በኋላ ፊልሙን ሳይሰራ ቀርቷል በሚል “የማጭበርበር” ክስ እንደሆነ ተገልጿል።

ከሳሽ ወ/ሮ ቤተልሄም አበበ የካቲት 6 ቀን 2006 ዓ.ም ጽፋ ለፍርድ ቤቱ ያቀረበችው ባለ 5 ገጽ የክስ ማመልከቻ፣ 2 ገጽ የማስረጃ ዝርዝር፣ 2 ገጽ ልዩ ልዩ ማስረጃዎች በድምሩ 9 ገጽ ክሱን የሚያስረዱ ወረቀቶች ከፍርድ ቤት ማዘዣ ጋር ለአርቲስት ዳንኤል የደረሰው ሲሆን አርቲስቱም መጋቢት 22 ቀን 2006 ዓ.ም በጠበቃው በኩል መረከቡን በፊርማ አረጋግጧል።

በዚህም መሠረት ዳንኤል ለቀረበበት ክስ ሚያዝያ 3 ቀን 2006 ዓ.ም ለከፍተኛው ፍርድ ቤት በሬጅስራር ጽህፈት ቤት በኩል ማስረጃውን እንዲያቀርብና እንዲሁም ግንቦት 12 ቀን 2006 ዓ.ም ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ጉዳዩ በችሎት እንዲታይ ፍርድ ቤቱ አዟል።
Daniel Tegegne

ዘ-ሐበሻ ይህን ጉዳይ ተከታትላ ትዘግባለች።

በባህር ዳር በተነሳ ግጭት ፖሊስ በጥይት ሕዝብ በድንጋይ ተከታከቱ፤ የሞቱም የቆሰሉም አሉ

$
0
0

(የባህር ዳር ከተማ)

(የባህር ዳር ከተማ ፎቶ ፋይል)


ለዘ-ሐበሻ ከባህዳር የደረሱ መረጃዎች እንዳመለከቱት ዛሬ በከተማዋ በፖሊስና በህብረተሰቡ መካከል በተደረገ የተኩስና የድንጋይ ውርውራ ልውውጥ ሰዎች ሞተዋል፤ የቆሰሉም አሉ፡፡ ፖሊስና ልዩ ሃይል በጥይት፤ ሕዝቡ በድንጋይ ባደረጉት መከታከት ከፖሊስም እንዲሁ የቆሰሉ እንዳሉ ተገልጿል፡፡

ዜናውን ያደረሱን የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደሚሉት ተኩሱ ለተከታታይ ሶስት ሰዓታት የተደረገ ሲሆን ህዝቡ “ቤታችን ለአምስትና ስድስት ዓመታት ያህል ሰርተን እየኖርንበት ያለ እና ሌላ ተለዋጭ ቤት የሌለን በመሆኑ ወይ ተለዋጭ ቦታና ቤት ስጡን ወይም ደግሞ የትንሳኤን በዓል እንኳን እንዋል አታፍርሱብን፤ ሌላ መቀመጫ የለንም” ብሎ ሲጮህ ማፍረሱን ቀጥለው፤ በፖሊስ እና ሚሊሻ የታጀበው አፍራሽ ከህዝቡ ጋር ግጭት ጀምሮ… የተኩስ እሩምታ ህዝቡ ላይ መተኮስ በመጀመራቸው ህዝቡም ምላሽ በመስጠት ሲብሰውም ወንጭፍ በመጠቀም ሴቱም ወንዱም አንድ ላይ ሆነው ትንሽ ትልቅ ሳይል ተማምለው በመውጣት ከፖሊስ ጋር ፖሊስ በጥይት ህዝቡም በድንጋይና ባገኘው ሁሉ ተኩስ ሲለዋወጡ ለሶስት ሰዓታት ቆይተዋል፡፡

እንደ መረጃዎቹ ገለጻ በርካቶች ቆስለዋል ከፖሊስም ከህዝቡም፡፡ በኋላም ፖሊስ ህዝቡን ሲያባርር ህዝቡ እደገና ፖሊስን ሲያባርር ከቆዩ በኋላ ህዝብ ፖሊሱን ሁሉ እያባረረ ወደ መሃል ከተማው ቀበሌ አስራ ሶስት ጎፋ አካባቢ ሲደርሱ የመጣው ልዩ ሃይል ህዝቡ ላይ አስለቃሽ ጭስ በመጠቀም ለመበተን ቢሞክሩም ሳይችሉ ቀርተው ህዝቡ በአንድ ሆሆሆ ብሎ በመሄድ ልዩ ሃይሎችንም በድንጋይና ጠርሙስ መቀጥቀጥ ይጀምራል፡፡

በዚህ ሰዓት የሞቱና የቆሰሉ በርካታ ናቸው ለጊዜው ቁጥራቸው አልደረሰንም፤ ከባህርዳር ያለው ምንጫችን ሲልክልን ለህዝብ እናደርሳለን፡፡ ፖሊስም ግሬደር በመያዝ ችግሩ ወደተፈጠረበት አካባቢ በመሄድ አያሌው ጎበዜ የሚባለውን ሰፈር እስከ ቤት እቃዎቻቸው ድረስ ጠራርጎ በማፈራረስ እና በአካባቢው የሚንቀሳቀስን ወጣት በሙሉ ለቃቅመው በማሰር ላይ ሲሆኑ አልፎ አልፎም የተኩስ ድምፅ ይሰማል፡፡

ፖሊስ ሴቶችንም ወንዶችንም ሽማግሌ ህፃን ሳይል በማሰር ላይ የሚገኝ ሲሆን የአካባቢው ወንዶች የት እንደደረሱ የታወቀ ነገር የለም። ሚስቶቻቸው እህት እናቶቻቸው አባት ወንድሞቻቸው በአጠቃላይ እዛ አካባቢ ያለው ሁሉ ወደ እስር ቤት ተግዘዋል፡፡ ይህ ተኩስ ልውውጥ ላይ እንደ አይን እማኞች ከሆነ ከበርካታ የባህርዳር ቀበሌዎች የተሰባሰበ ህብረተሰብ ከሰፈሩ ሰዎች ጋር በመተባበር ፖሊስና ልዩ ሃይልን በጋራ ሲያባርር እንደነበር ገልፀዋል፡፡

በዛሬው የባህርዳሩ ግጭት ለጊዜው የአባቱ ስም ያልታወቀ ጨመረ የተባለ ወጣት ግንባሩ ላይ በጥይት ተመትቶ አስከሬኑ ወደ ሆስፒታል ሲወሰድ ፖሊሶች ቀምተው አስከሬኑን አንሰጥም ማለታቸውም ተሰምቷል።

ለዘ-ሐበሻ መረጃውን ያደረሱ ወገኖች እንዳሉት ይህ ግጭት ለጊዜው አሁን ትንሽ ጋብ ያለ ቢሆንም አልፎ አልፎ በዚህ ሰዓትም ተኩስ ድምፅ ይሰማል፡፡ እነዚህ አካባቢዎች እና ቀበሌዎች “ለፖሊስ ኢፍትሃዊ ድርጊት አንገዛም፤ ላቤን ጠብ አድርጌ አፈር ቆፍሬ ደክሜ የሰራሁትን ቤት ሲያሰኝህ እየመጣህ ልታፈርሰው አትችልምም፣ ፈቃድ አውጥቼ ስንት ጊዜ በሙሰኛ ባለስልጣናት ተበዝብዤ የሰራሁትን ቤቴን ሌላ መውደቂያ ሳይኖረኝማ አታፈርሰውም” ብለው ለበርካታ አመታት ሲደክሙ ቆዩትን ቤት በሌሊት እንደ ሽፍታ የማፍረሻ ትዕዛዝ ሳያሳዩ ለማፍረስ መሞከር ህገወጥነት ሆኖ እያለ የንፁሃንን ደም በከንቱ ማፍሰስ የመንግስትን ወሮ በላነትና የፖሊስን ደደብነት የሚያሳይ አሮጋንተነት ነው ሲሉ አስተያየታቸውን የባህርዳር ነዋሪዎች ይሰጣሉ፡፡

ተጨማሪ ዘገባዎችን እንደደረሱን እንመለሳለን።

health: ስለኮሌስትሮል ሊያውቁ የሚገባዎት 6 ነገሮች

$
0
0

6. ኮሌስትሮልን በጥቂቱ

ኮሌስትሮል የሁሉም እንስሳት ህዋሳት አካል የሆነ የማይሟሟ ነጭ የቅባት አይነት ሲሆን በበርካታ የሰውነት ተግባራት ውስጥ ቁልፍ ስራዎችን ያከናውናል፡፡ ሆርሞን ዝግጅት ውስጥ አለ፤ ሰውነት ቫይታሚን ዲ መጠቀም እንዲችል በመርዳቱም ይታወቃል፡፡ የሴቶችና የወንዶችን ፆታዎች ሆርሞኖች ቴስቴስቴሮን እና ኤስትሮጅን እንዲሁም ሀይል አጠቃቀማችንን የሚያስተካክለው አድሬናል ሆርሞን ምርትም ግብአት ነው፡፡ ቅባት ነክ ምግቦችን ስንመገብ ለመፍጨት የሚያገለግለው ሀሞትም ከኮሌስትሮል ነው የሚዘጋጀው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የህዋሳቶቻችን ሽፋኖችም እንዲሁ ስሪታቸው ኮሌስትሮል ነው፡፡ ነርቭ ጫፎችን በመሸፈንም የነርቭ መልዕክቶች የተቀላጠፈ እንዲሆኑ ይረዳል፡፡
colesterol
ኮሌስትሮል ራሱ የሚዘጋጀው በዋናነት በጉበት ውስጥ ሲሆን አብዛኛዎቹ የሰውነት ህዋሳቶችም ኮሌስትሮልን ይሰራሉ፡፡ በደም ውስጥ ሊፖፕሮቲንስ በተሰኙ ተሸካሚዎች ይዘዋወራል፡፡

5. የኮሌስትሮል ምንጮች

ያለው በቂ በመሆኑም ከሰውነት ውጪ የሚመጣ ኮሌስትሮል አስፈላጊ አይደለም፡፡ ከውስጥ ተጨማሪ ምግብ አያስፈልግም፡፡ ይሁንና የምንወስዳቸው ምግቦች ውስጥ ቅባት ስለሚገኝ ጤናማውን ምጣኔ በአመጋገባችን ምክንያት እናዛባዋለን፡፡ ከእነዚህ ኮሌስትሮል በብዛት ከምንወስድባቸው ምግቦች መካከል እንቁላል፣ ስጋና ሌሎች ሙሉ ቅባት ያላቸው የእንስሳት ተዋፅኦ ውጤቶች ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ሁሉም ከእንስሳት የሚገኙ ምግቦች ኮሌስትሮልን የሚይዙ ሲሆን ከኮሌስትሮል ነፃ የሆኑት ከእፀዋት የሚገኙ ምግቦች ብቻ ናቸው፡፡
በተለይ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ከእንስሳት ተዋፅኦ የሚገኙት እንቁላል፣ ስጋ እና ቅቤ የምቾት ምግቦች ተብለው ስለሚቆጠሩ የሚበዛው ሰው ትንሽ ገንዘብ ሲያገኝ እነዚሁኑ ምግቦች ይሸምትና ይጠቀማል፡፡ በአሁኑ ወቅት ከተማ አካባቢ ብዙ መቀመጥ እና ኮሌስትሮል በዝቶ የሚገኝባቸውን ፈጣን ምግችና ጥብሳ ጥብሶችን የመመገብ ልምዶች እየሰፉ በመምጣታቸውም ኮሌስትሮል ጉዳቱ በቅጡ ሳይታወቅ ለበርካቶች የጤና ጠንቅ እየሆነ መምጣቱን ባለሞያዎች ይገልፃሉ፡፡

4. ጥሩ ኮሌስትሮል፣ መጥፎ ኮሌስትሮል

ኮሌስትሮል በሰውነት ውስጥ የሚዘዋወርበት ዋነኛ ሁለት መልክ ያለው ሲሆን አንደኛው ‹‹ጥሩ›› ሌላኛው ‹‹መጥፎ›› ተብለው በተለምዶ ይጠራሉ፡፡ መጥፎ የሚባለው አይነት የኮሌስትሮል መልክ ዝቅተኛ ግዝፈት ያለው ኮሌስትሮል ሲሆን ከጉበት ወደ ህዋሳት የሚደርሰው ኮሌስትሮል በዚህ መልክ ይገኛል፡፡ በደም ውስጥ መጠኑ ከልክ ሲያልፍ የደም መተላለፊያ መስመሩን ሊደፍን ስለሚችል ነው መጥፎ የተባለው፡፡ የደም ቧንቧዎቹ መደፈን ደግሞ ወደ ተለያዩ የሰውነት ክፍሎች የሚደርሰው ደም እንዲገታ እና ለልብ እና የደም ቧንቧ በሽታዎች እንድንጋለጥ ያደርጋሉ፡፡
ጥሩው የሚባለው ከፍተኛ ግዝፈት (ዴንሲቲ) ያለው ኮሌስትሮል መልክ የደም ቧንቧዎችን ጨምሮ በህዋሳት ውስጥ የተጠራቀመውን ትርፍ ኮሌስትሮል መጥጦ ወደ ጉበት የሚያስወግድ በመሆኑ በጥሩነቱ ይነሳል፡፡ ጥሩም መጥፎም ለመባል መጠኑ ወሳኝ መሆኑን የሚናገሩት ባለሞያዎች የኮሌስትሮል ልኬትን ተለክቶ ማወቅና ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ጨምረው ይገልፃሉ፡፡

3. ጤናማ የኮሌስትሮል
መጠን ምን ያህል ነው?

ኮሌስትሮል ለተለያዩ የሰውነት ወሳኝ ተግባራት አስፈላጊ እንደመሆኑ በሰውነት ውስጥ እንዲገኝ ያስፈልጋል፡፡ ነገር ግን ምን ያህል ኮሌስትሮል ያስፈልገናል የሚለው እና መጠኑም በጤናማ ክልል ውስጥ ስለመገኘቱ እርግጠኛ መሆን ያስፈልጋል፡፡ ጤናማ የኮሌስትሮል መጠን በሐኪሞቹም ዘንድ ቁርጥ ያለ ቁጥር የሚቀመጥለት አይደለም፡፡ በአማካይ ግን በደም ውስጥ የሚገኝ የኮሌስትሮል መጠን በሊትር ከ5.5 ሚሊሞል መብለጥ እንደሌለበት ስምምነት አለ፡፡ ይህ መጠን የሚፈቀደው ግን ሙሉ ጤነኛ ለሆኑና በተለያዩ ምክንያቶች ለልብና ተያያዥ ህመሞች ተጋላጭነት ለሌላቸው ሰዎች ነው፡፡ ፆታ፣ ዕድሜ፣ በቤተሰብ ውስጥ ያለ የልብ ህመም ታሪክ፣ ሲጋራ የማጨስ ልምድ፣ ከልክ ያለፈ ክብደት እንዲሁም ከፍተኛ የደም ግፊት ወይም ስኳር ህመም በመጠኑ ላይ ተፅዕኖ ይኖራቸዋል፡፡ ከላይ ከተጠቀሱት በሁለት ወይም ከዚያ በላይ ሁኔታዎች በአንድ ሰው ላይ የሚስተዋሉ ከሆነ ዝቅተኛ ግዝፈት ያለው ኮሌስትሮል (መጥፎ ኮሌስትሮል) መጠን ከ2.5 ሚሊሞል በሊትር መብለጥ አይኖርበትም፡፡
በመሆኑም የአንድ ሰው የኮሌስትሮል መጠን በተለያዩ ተጨማሪ አጋዥ ምክንያቶችም የሚወሰን በመሆኑ ለሁሉም ሰው የሚሰራ ምጣኔ ማስቀመጥ በባለሞያዎቹ አይመከርም፡፡ ይህ ግለሰብ በሐኪም ታይቶ ሊወሰን የሚገባ እንደሆነም ይጠቆማል፡፡ ነገር ግን ማንም በሊትር ከ6 ሚሊሞል በላይ ኮሌስትሮል በደሙ የሚገኝ ሰው በባለሞያ ክትትል ሊደረግለት ይገባል፡፡

2. የኮሌስትሮል ጠንቆች

በሰውነት ውስጥ ኮሌስትሮል በጉበት ውስጥ ስለሚመረት ተጨማሪ ኮሌስትሮል ከምግብ ማግኘት አስፈላጊ አይደለም፡፡ ሰውነት ለራሱ ተግባራት በቂ ኮሌስትሮል ያዘጋጃል፡፡ ይሁንና የተለያዩ የእንስሳት ተዋፅኦ ምግቦችን በምንመገብበት ወቅት የምንወስዳቸው ቅባቶች በሰውነታችን ከተመረተው ኮሌስትሮል ጋር በጉበት አማካይነት ተቀላቅለው በሊፕሮቲን መልክ ወደ ደም ዝውውር ስርዓት ይቀላቀላሉ፡፡
በደም ዝውውር ውስጥ የእነዚህ ውህዶች መጠኑን ባለፈ ሁኔታ መገኘት ቅባቶች በደም ቧንቧዎች ውስጥ እንዲጠራቀሙ ያደርጋል፡፡ ይህ የቧንቧዎች በቅባት መጠቅጠቅ ቧንቧው እንዲጠብ ቀስ እያለም ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ ያስገድደዋል፡፡ የደም ፍሰቱ መገታት ለከፋ የልብ ህመም እንዲሁም በጭንቅላት የደም መቋረጥ (ስትሮክን) ይዞ ይመጣል፡፡ ስትሮክን ተከትሎ በሚገጥም የመውደቅ፣ የነርቮች መዛበት አሊያም ስራ ማቆም የበረቱ የጤና ችግሮች ይከሰታሉ፡፡

1. ኮሌስትሮልን መቆጣጠሪያ ስልቶች

ኮሌስትሮል የጤና እክል ከመፍጠሩ በፊት መቆጣጠር መከላከል ይቻላል፡፡ ዋነኞቹ መንገዶችም ከአመጋገብ እና የአኗኗር ስታይል ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡ ቅባት ያላቸውን የተጠበሱ ስጋ እና የስጋ ውጤቶችን መመገብ ይቀንሱ፡፡ የድንች ጥብስ (ቺፕስ)፣ በርገር በተለይ ቺዝ በርገር፣ ኬክ ብስኩትና አጠቃላይ ጥብሳ ጠብሶች የኮሌስትሮል ምንጭ በመሆናቸው ከእነዚህ በሚቻል መጠን መራቅ ይመከራል፡፡

ከምግብ እና መጠጦች በተጨማሪ በሰውነት ውስጥ ያለን የኮሌስትሮል ምጣኔ በመቆጣጠር በኩል የእለት ተዕለት ልምዶችና ባህሪያቶቻችንንም ወሳኝ ናቸው፡፡ አልኮል መጠጦች በተለይ ተቀላቅለው የሚጠጡ መጠጦች የደም ኮሌስትሮልን ሊጨምሩ ስለሚችሉ በቀን ከሁለት በላይ እንዲጠጡ አይመከርም፡፡ ሲጋራም ይከለከላል፡፡ ሲጋራ አደገኛ የሚባለውን ዝቅተኛ ግዝፈት ያለው ኮሌስትሮል ወደ ደም ቧንቧ እንዲገባ በማመቻቸቱ ስለሚታወቅ ሲጋራ አያጭሱ ሲሉ ባለሞያዎቹ ይናገራሉ፡፡ የአካል ብቃት እንቀስቃሴ ጥሩውን ኮሌስትሮል መጠን በሰውነት ውስጥ የጨመረም ጥቅም ስላለው በሳምንት ቢያንስ ለ3 ቀናት ለ30 ደቂቃ ፈጣን እርምጃ ቢያደርጉ እንኳ ኮሌስትሮል ምጣኔን በከፍተኛ ሁኔታ መቆጣጠር ይችላሉ፡፡ ክብደትዎ በጤናማ ክልል ውስጥ እንዲሆን ይጣሩ፣ የስኳር መጠንዎን መቆጣጠርም ይመከራል፡፡ የእንስሳት ተዋፅኦ ምግቦች ኮሌስትሮል ስላላቸው ተቆጣጠሯቸው ሲባል አይመገቡ ማለት አይደለም፡፡ እነዚህ የምግብ አይነቶች ለሰውነት ጠቃሚ የሆኑ እንደ ካልሲየም አይነት ንጥረ ነገሮች ስለሚይዙ መጠናቸውን አያብዙ እንጂ ጨርሰው አያስወግዷቸው፡፡

በምግብ እንዲሁም በአኗኗር ስታይል ጤናማነት ኮሌስትሮልን መቆጣጠር ቢቻልም ይህ ይከብደኛል ላሉት ምዕራባውያን የኮሌስትሮል መቀነሻ መድኃኒቶች ተሰርተው ያለ ሐኪም ትዕዛዝ ከፋርማሲዎች ይሸጥላቸዋል፡፡ የተሻለው ግን ባለሞያ ጋር ቀርቦ ምርመራ እና እርዳታ ማግኘት ተመራጩን መፍትሄም መከተል ተመካሪ ነው፡፡ የአመጋገብ እና አኗኗር ልምዳችን ግን በእጃችን ነውና ጥንቃቄ አይለየን፣ ጤና ሁኑ!


የኢትዮጵያ መንግስት በረዳት አብራሪ ኃይለመድህን አበራ ላይ ክስ መሰረተ (ተመስገን ደሳለኝ)

$
0
0

-ከ253, 336 ከ42 ሳንቲም ዩሮ በላይ ኪሳራ ደርሷል ተብሏል
-የአእምሮ ችግር እንዳሌለበትም ተረጋግጧል

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ፍትሕ ሚኒስቴር በረዳት አብራሪ ኃይለመድን አበራ ላይ የካቲት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ሌሊት የበረራ ቁጥር ET 702 የሆንን ቦይንግ አውሮፕላንን ከእነ 202 ተሳፋሪዎቹ ወደ ሮም በሚበርበት ወቅት ጠልፎ ሲውዘርላንድ አሳርፏል በማለት በከፍተኛው ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ክስ መመስረቱን የፍትሕ ሚኒስቴር ምንጮቼ አረጋግጠውልኛል፡፡
በኃይለመድን ላይ የቀረበው ክስ ሁለት ሲሆን፤ የመጀመሪያው በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 507/1/ ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፡-
‹‹…በዋና አብራሪ ፓትዮዝ ባርቤሪ አማካኝነት ከአዲስ አበባ በሱዳን በኩል ወደ ጣሊያን ሀገር ሮም ከተማ መንገደኞችን ለማድረስ በማጓጓዝ ላይ እንዳለ ዋናው አብራሪው የበረራ መቆጣጠሪያውን ክፍል ከውስጥ በመቆለፍ፣ ያለፍቃድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ አውሮፕላኑን በቁጥጥር ሥር በማድረግ የአውሮፕላኑ የበረራ ቡድን አባላት በሩን እንዲከፍት ሲጠይቁት አርፋችሁ የማትቀመጡ ከሆነ በአውሮፕላኑ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ ብሎ በማስፈራራት፤ እንዲሁም የአውሮፕላኑን የመዳረሻ አቅጣጫ ያለአግባብ በማስቀየር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ፈቃድ ውጭ ወደ ስዊዘርላንድ አየር ክልል ውስጥ በመግባት ተሳፋሪዎች እና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ሕይወት እና ደህንነት አደጋ ላይ እንዲወድቅ አድርጎ በመጨረሻ በጄነቭ ከተማ ውስጥ ያለመዳረሻው እንዲያርፍ በማድረጉ እና ተሳፋሪዎችን ለአደጋ በማጋለጡ በፈፀመው በሕገ-ወጥ መንገድ በጉዞ ላይ ያለን አውሮፕላን መያዝ ወይም ማገት›› የተከሰሰ መሆኑን ያትታል፡፡
በሁለተኛነት የተመሰረተብት ክስ ደግሞ በዚሁ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 508/1/ ላይ ያለውን መተላለፍ የሚል ሲሆን፤ ክሱም በአጭሩ እንዲህ ይላል፡-
‹‹…ያለፍቃድ እና በሕገ-ወጥ መንገድ አውሮፕላኑን በቁጥጥር ሥር በማድረግ የአውሮፕላኑ የበረራ ቡድን አባላት በሩን እንዲከፍተው ሲጠይቁት አርፋችሁ የማትቀመጡ ከሆነ በአውሮፕላኑ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ በማለት በማስፈራራት አውሮፕላኑን በድንገት እና በፍጥነት ሁለት ጊዜ ከፍ እና ዝቅ (dive) በማድረግ በአውሮፕላኑ ውስጥ ያሉትን የመንገደኞች ምግብ ማቅረቢያ ቁሳቁሶች እንዲገለባበጡ በማድረግ፣ የአውሮፕላኑን የመዳረሻ አቅጣጫ ያለአግባብ በማስቀየር፣ ከአትዮጵያ አየር መንገድ ፈቃድና እውቅና ውጭ ስዊዘርላንድ አየር ክልል ውስጥ በመግባት ስዊዘርላንድ ከተማ ጀኔቭ በመግባት አየር ላይ በማንዣበብ ከቆየ በኋላ እንዲያርፍ በማድረግ በፈፀመው በሕገ-ወጥ መንገድ በጉዞ ላይ ያለን አውሮፕላን አስጊ ሁኔታ ላይ መጣል ወንጀል ተከሷል፡፡››

ኃይለመድህን አበራ

ኃይለመድህን  አበራ

በፌ/አቃቤ ሕግ ብርሃኑ ወንድምአገኝ ፊርማ ለፍርድ ቤቱ የቀረበው ማመልከቻ ከስ ቻርጁን ጨምሮ አስራ አንድ ገፅ ሲሆን፤ የዋና አብራሪው፣ የአምስት የበረራ አስተናጋጆች እና የአራት ሰዎች ስም ዝርዝር በመስክርነት ተገልፆአል፡፡ በሰነድ ማስረጃነት ደግሞ አየር መንገዱ በ27/6/06 ዓ.ም ለፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ የጻፈው አራት ገጽ እና ሲቪል አቬየሽን በ21/6/06 ኃይለመድንን በተመለከተ የጻፈው ማብራሪያ ከነአባሪው ሁለት ገጽ ቀርቧል፡፡
የኃይለመድን አበራን የጤንነት ሁኔታ በተመለከተ አየር መንገዱ ለፌደራል ፖሊስ በላከው ደብዳቤ በስድስት ወር ውስጥ አምስት ጊዜ ያህል ለቀላል ሆድ ቁርጠት፣ ራስ-ምታት፣ ጉንፋንና ተቀምጥ ወደ ድርጅቱ ክሊንኪ ከመሄዱ ያለፈ ምን ችግር ያሌለበት ጠኔኛ እንደሆነ ገልፆአል፡፡ ሲቪል አቬሽንም በተመሳሳይ መልኩ በላከው ደብዳቤ አብራሪው አመታዊ የጤና ምርምራ አድርጎ እ.ኤ.አ. እስከ 22/12/2014 ዓ.ም ድረስ ጤነኛ መሆኑን ማረጋገጫ ሰርተፍኬቱን አድሶ እንደሰጠው አስታውቋል፡፡ አየር መንገዱ ከዚሁ ጋር አያይዞ ሁለት መቶ ሀምሳ ሶስት ሺህ፣ ሶስት መቶ ሰላሳ ስድስት ብር ከአራባ ሁለት ሳንቲም ዩሮ ኪሳራ እንደደረሰበት እና በቀጣይም ተጨማሪ ክፍያዎች እንደሚኖሩበት ገልፆአል፡፡ እንደ ምንጮቼ አገላለፅ መንግስት ክሱን በሚስጥር የያዘው ሲሆን፤ እስካሁንም በሚቆጣጠራቸው ሚዲያዎቹ ላይ ጉዳዩን በዜና እንዲገለፅ አላደረግም፡፡
የሆነው ሆኖ ዋናው ጥያቄ ኃይለመድን ጠለፋውን ባፈፀመበት ወቅት ‹‹እብድ›› (የአእምሮ ችግር ያለበት) ለማስመሰል የተደረገው ሙከረ ውሸት እንደሆነ በአየር መንገዱና በሲቪል አቬሽን ተፅፈው ከክሱ ጋር የተያያዙት ደብዳቤዎች በማረጋገጣቸው፣ የጠለፋው ምክንትያት ምንድን ነው? የሚለው ይመስለኛ፡፡ በርግጥ ምንም እንኳ ምክንያቱን አብራሪው በሲዊዘርላንድ ፍርድ ቤት ቀርቦ እሲኪናገር መጠበቅ እንዳለብኝ ባልዘነጋም፤ በግሌ እጅግ አፋኝና ነውረኛ የሆነው ሥርዓት ላይ ያለውን ተቃውሞ ለመግለፅ ያደረገው ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ይህ እውነት ከሆነ ደግሞ ኃይለመድንን ሊወቀስና ሊወገዝ የሚችልበት ነገር የለም፡፡ አየር መንገዱ የሕዝብ መሆኑ ባይካድም፤ በአሁኑ ወቅት የጥቂት ጉምቱ ባለሥልጣናት መፈንጫ እና ኪስ ማደለቢያ መሆኑ መዘንጋት የለበትምና፡፡፡
ከዚህ አንፃርም ከሀገር ውጪ ላሉ ወገኖቼ ሁለት መልዕክት ማስተላለፍ እወዳለሁ፡፡ የመጀመሪያው የኃይለመድን ስልት ዞሮ ዞሮ በሰላማዊ ትግል ማዕቀፍ ውስጥ መውደቁ የማይቀር ነውና፣ ጉዳዩ በጀብደኝነት አሊያም የተሳፋሪዎችን ደህንነት አደጋ ላይ በማይጥልና ኃላፊነት በሚሰማው፣ ሙያውንም ሆነ የወሰደው እርምጃ የሚኖረውን ውጤት አስቀድሞ በሚያውቅ የተፈፀመ በመሆኑ ዓለም አቀፍ ማሕበረሰቡ ላይ ግፊት በማድረግና ጉዳዩ ጭቆናን ከመቃወም ጋር እንደሚየያዝ በማሳመን ከተጠያቂነት የሚድንበትን መንገድ ማፈላለግ ላይ ማተኮር ሲሆን፤ ሁለተኛው ኢህአዴግ እስርኞችን በማሰቃየት ግንባር ቀደም በመሆኑ ተላልፎ እንዳይሰጠው ከጎኑ መቆም ማድረግ ላይ እንድታተኩሩ (ምናልባት ከክሱ ጋር የተያያዙ ማስረጃዎች የምትፈልጉ የሕግ ባለሙያዎች እዚህ ጋ በአታችመንት ከተቀመጡት ዶክመንቶች በተጨማሪ በኢሜል ልልክላችው እችላለሁ)
በመጨረሻም የግፍ አባት የሆነውን ነውረኛ ሥርዓት ለመቀየር (አማራጮቹ እየጠበቡ በመሄዳቸው) እንዲህ አይነት መንገዶችንም ግምት ውስጥ ማስገባት የግድ እንደሆነ መረደት ይኖርብናል፡፡
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

 

የባልቻ አባነፍሶ ልጆች እንሁን ! (ሚሊዮኖች ድምጽ)

$
0
0

 ነጻነት ዋጋ ያስከፍላል። አገር ቤት ያሉ ወገኖቻችn እጅግ በጣም ከባድና ፈታኝ በሆነ ሁኔታ ለሰላም፣ ለዴሞክራሲ፣ ለሕግ የበላይነት ፣ ለነጻነትና ለኢትዮጵያ አንድነት፣ እልህ አስጨራሽ ትግል እያደረጉ ነው። «ሽብርተኞች ናቸው» በሚል በቃሊት ፣ በቂሊንጦ፣ ዝዋይ በመሳሰሉ ዘግናኝ እሥር ቤቶች እየማቀቁ ያሉ ፣ የሰላምና የዴሞክራሲ አርበኞች የሆኑ፣ ብርቅዬ የኢትዮዮጵያ ልጆችን መመልከቱ ይበቃል። አንዱዋለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንን፣ በቀለ ገርባ፣ እስክንድር ነጋ ፣ ርዮት አለሙ እያለን ብዙ መዘርዘር እንችላለን።

Balcha ljoch

ከጥቂት ሳምንታት በፊት በአንድ በሩጫ ላይ «ረብሻቹሃል» በሚል ፖሊሲ ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ፣  ሰባቱን  የ«ጣይቱ ልጆች» አስሮ ማንገላታቱ በስፋት ተዘግቦ ነበር። በዚህ ሳምንትም፣  የአዲስ አበባ ፖሊሲ፣ ሕዝብን ለመጠበቅና ለማገለገል ሳይሆን፣ ሕዝብን ለማወክና ለማሸበር የተሰማራ እንደሆነ በድጋሚ ያረጋገጠበት ሁኔታ ነዉ የነበረው።

ዘጠኝ  የአንድነት አባላት፣  ሕገ መንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት፣ መጋቢት 28 ቀን ሊደረግ ታስቦ ለነበረው ሰላማዊ ሰልፍ፣ በራሪ ወረቀት በማደል ቅስቀሳ ያደርጋሉ። አልፈሩም። አልደነገጡም። «ሰው ያለ ነጻነቱ ምንድን ነው ?» በሚል፣ ጀግንነታቸውን አሳዩ።  አራቱ ወንድሞቻችን ከፍተኛ ድብደባ ሲደርስባቸው፣ ሁለቱ የረሃብ አድማ አድርገው ከአምሰት ቀናት እሥር በኋላ ይፈታሉ።  ሶስቱ፣ ምንም እንኳን ፍርድ ቤቱ ምንም ወንጀል አልተገኘባቸው የሚል ድምዳሜ ቢደርስም፣ አንድ ሺህ ዶላርና የመንግስት ሰራተኛ ዋስ አቅርቡ በማለቱ፣  እስከአሁን በእሥር ላይ ናቸው።

እነዚህ ዘጠኙ የአንድነት አባላት፣ በድፍረታቸውና በቆራጥነታቸው በርግጥ የባልቻ አባ ነፍሶ ልጆች መሆናቸውን በገሃድ አሳይተዋል። ባደረጉት ሥራ እና በከፈሉት መዋእትነት ትግል ማለት ምን ማለት እንደሆነ አሳይተዉናል።

አዎን ነጻነት ዋጋ ያስከፍላል። አገራችን ኢትዮጵያ ሕግ የበላይ የሆነባት፣. ዜጎቿ በሁሉም የአገሪቷ ክፍል ሳይፈሩ፣ ሳይሸማቀቁ የሚኖሩባት፣ ሰብአዊ መብት ያለ ገደብ የሚከበርባት፣ አንድነቷና ሉአላዊነት የተጠበቀና የበለጸገች ኢትዮጵያ እንድትሆን ከፈለግን፣  ዘጠኝ አይደለም፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የጥይቱ ልጆች፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የባልቻ አባ ነፍሶ ልጆች ያስፈልጋሉ።

የሚሊዮኖች ድምጽ እንቅስቃሴ ተጀጀመረ እንጂ አላለቀም። በባህር ዳርና በደሴ፣ የታየው ጅማሬ እንጂ ፍጻሜ አይደለም። ከአገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ የምንኖር ኢትዮጵያውያን ሁሉ መነቃነቅ እንዳለብን ለማሳሰብ እንወዳለን። ባለለንበት ቦታ እንደራጅ። እንዴት መሳተፈ፣ እንዴት መርዳት እንዳለብን እንመካከር። ትግሉ የአንድነት ድርጅት ሳይሆን የሚሊዮኖች ነው። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን። የጣይቱ ልጆች፣ የባልቻ አባ ነፍሶ ልጆች እንሁን።

የአዲስ አበባዉ ቅስቀሳ ከተጀመረ ከመጋቢት 25 ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 2 ድረስ የነበረዉን ፣ በባልቻ አባ ነፍሶ ልጆች የደረሰዉን  ለማንበብ ከታች ይመለከቱ። በገንዘብ መርዳት የምንፈልግ  http://www.andinet.org

በመሄድ በፔይፓል  መርዳት አስተዋጾ ማድረግ እንችላለን። ተጨማሪ ማብራሪ ካስፈለገም  millionsforethiopia@gmail.com በሚለው አድራሽ ኢሜል ቢያደርጉልን ሊያገኙን ይችላሉ።

 ከመጋቢት 25 እስከ ሚያዚያ 2  የባልቻ አባ ነፍሶ ልጆች  ሁኔታ እንደሚከተለው ይከታተሉ

ሐሙስ መጋቢት 25 ቀን 2006 ዓ.

በለገሃር አካባቢ ሲቀሰቅሱ የነበሩ፣  ወጣት አክሊሉ ሰይፉና ሰለሞን ፀሐዬ፣  በለገሃር ፖሊስ ጣቢያ ከፍተኛ ድብደባ ይፈጸምባቸዋል። ሲ.ኤም.ሲ አካባ፣  ኤፍሬም ሰለሞን እና ታሪኬ ኬፋ በተመሳሳይ ሁኔት በፖሊስ ይደበደባሉ። በየካ ክፍል ከተማ፣ እውቁ ደራሲ መቶ አለቃ አንዳርጌ መስፍን፣ ሃብታሙ ታምሩና አሸናፊ ጨመዳም ሕግ መንግስቱ የሚፈቅድላቸውን መብት ተጠቅመው ሰላማዊ የቅስቀሳ በራሪ ወረቀት ሲያሰራጩ በፖሊስ ይታሰራሉ።በቂርቆስ ክፍለ ከተማ፣ በካሳንሺስ አካባቢ፣  ወርቁ እንድሮ እና አክሊሉ ሰይፉ በተመሳሳይ ሁኔታ ታስረዉ ወደ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ይወሰዳሉ። በዚችዉ አንድ ቀን ብቻ አራት የአንድነት አባላት ሲደበደቡ አምስት ወደ ወህኒ ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ ተወስደዋል።

ዓርብ መጋቢት 26 ቀን 2006 ዓ.

የአንድነት አመራር አባላት ፖሊሶች የታሰሩት እንዲፈቱ፣ ታሳሪዎቹ ሕግን አክብረዉ በሰላማዊ መንገድ ፓርቲው መመሪያ ሰጧቸው የቀሰቀሱ እንደሆነ ለማስረዳት ቢሞክሩም እስረኞቹ «ከአዲስ አበባ ፖሊስ መምሪያ በስማችን ደብዳቤ ካልተፃፈልን አንለቃቸውም» በሚል፣ ፍርድ ቤት ሳይወስዷቸው፣ ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ ዜጎች ለሁለተኛ ቀን በወህኒ እንዲቆዩ አድርገዋል።

ቅዳሜ መጋቢት 27 ቀን   2006 ዓ.

አሁንም እስረኞች ክስ ሳይመሰረትባቸው ለሶስተኛ ቀን በእስር እንዲቆዩ ይደረጋል።

እሁድ መጋቢት 28 ቀን    2006 ዓ.

እስረኞቹ ለአራተኛ ቀን ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ ፣ በእስር አሁን ይቆያሉ።

ሰኞ መጋቢት 29 ቀን  2006 ዓ.

አንድነት ፓርቲ ለመጋቢት 28/2006 ጠርቶት በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ለህዝብ የተዘጋጀ በራሪ ወረቀት ሲበትኑ በህገ ወጥ መንገድ በቁጥጥር ስር ከዋሉት የአንድነት ፓርቲ አባላት መካከል በስድስተኛ ፖሊስ ጣብያ የሚገኙት፣ አክሊሉ ሰይፉና ወርቁ እንድሮ መታሰራቸውን በመቃወም የርሃብ አድማ ይመታሉ።

አክሊሉን እና ወርቁ ጨምሮ በየካ ክፍለ ከተማ የታሰሩ ሌሎች ሶስት የአንድነት አባላትም ለአምስተኛ ቀን እንዲታሰሩ ይደረጋል።

ማክሰኞ መጋቢት  30  2006 ዓ.ም  

‹‹የእሪታ ቀን›› ሰላማዊ ሰልፍ ለህዝብ የተዘጋጀ በራሪ ወረቀት ሲያሰራጩ ከተያዙት አምስት የአንድነት አባላት መካከል ስድስተኛ ፖሊስ ጣብያ የነበሩትና የርሃብ አድማ የመቱት ወርቁ እንድሮና አክሊሉ ሰይፉ ፖሊስ በትናንትናው ዕለት፣ ከአምስት ቀናት እሥር በኋላ ያለምንም ዋስትና ይለቃቸዋል።

በየካ ክፍል ከተማ የታሰሩ መቶ አለቃ አንዳርጌ፣ ሃብታሙ ታምሩና አሸናፊ ጨመዳ ግን ለስድስተኛ ቀን በ እሥር እንዲቆዩ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ በ እስር እኒቆዩ ይደረጋል።

ረእቡ  ሚያዚያ 1   2006 ዓ.

የካ ፖሊስ ጣብያ የታሰሩት መቶ አለቃ አንዳርጌ መስፍን፣ ሃብታሙ ታምሩና አሸናፊ ጨመዳ በማለዳዉ የካ ምድብ ችሎት ቀርበው ለነገ ተለዋጭ ቀጠሮ ይሰጣቸዋል።

የየካ ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ክስ ‹‹ተጠርጣሪዎቹ ያለ ፓርቲው ፈቃድ ወረቀት በመበተን አመጽ እንዲነሳ አድርገዋል፣ሌሎች ተባባሪዎቻቸውም ስላልተያዙ እነርሱን በመያዝ ምርመራዬን እንዳጠናክር ተጨማሪ የሰባት ቀን ቀጠሮ ይፈቀድልኝ ››ብሏል፡፡ችሎቱን ለመከታተል በቦታው ተገኝተው የነበሩት የአዲስ አበባ የአንድነት ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ አቶ ነብዩ ባዘዘው፣ ፍርድ ቤቱን በማስፈቀድ‹‹እነዚህን ሰዎች ወረቀት እንዲበትኑ አመራር የሰጠናቸው እኛ ነን፡፡ፖሊስ እነርሱን ፈትቶ እኛን ይሰር ››ከማለታቸውም በላይ‹‹የአዲስ አበባ መስተዳድር ላቀረብንለት የእውቅና ጥያቄ የዘገየ ምላሽ በመስጠቱና ቀኑ እየተቃረበ በመምጣቱ ህዝብ የማስተባበር ስራ እንዲሰራ አድርገናል፡፡መስተዳድሩ የሰልፉን ቀን እንድንቀይር የጠየቀን አርብ ዕለት ነው፡፡አባላቶቻችን ግን የታሰሩት ሐሙስ ዕለት ነው ፡፡ወረቀቱ ከደረሰን በኋላ የቅስቀሳ ስራችን አቁመን ህጉን አክብረናል፡፡ፖሊስ ግን ወገንተኛ ሆኖ አባላቶቻችንን አስሮ እያጉላላ በመሆኑ ያለምንም ዋስትና እንዲፈቱልን እንጠይቃለን››ብለዋል፡፡

ዳኛ ማሞ ሞገስ ፖሊስ ከአዲስ አበባ መስተዳድር የተጻፈውን ደብዳቤ በመመልከት እንዲወስን አመጽ እንዲነሳ ስለመስራታቸው መረጃ አለኝ የሚል ከሆነም ለነገ እንዲያቀርብ ያዛሉ። እስረኞች ለሰባተኛ ቀን በወህኒ እንዲቆዩ ይደረጋል።

 

 ሐሙስ ሚያዚያ 2 ቀን  2006 ዓ.

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሶስት አባላት መቶ አለቃ አንዳርጌ መስፍን፣ሐብታሙ ታምሩና አሸናፊ ጨመዳ በዛሬው ዕለት የካ ምድብ ችሎት ቀርበው አስገራሚ ዋስትና ይጠየቅባቸዋል።

ፓርቲው የ‹‹እሪታ ቀን› በማለት ለሰየመው ሰላማዊ ሰልፍ መገናኛ አካባቢ በራሪ ወረቀት ሲበትኑ የዛሬ ሳምንት በህገ ወጥ መንገድ የተያዙት የፓርቲው አባላት በዛሬው ዕለት ለሶስተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡የፓርቲው አመራሮችና አባላት የትግል አጋሮቻቸውን ጉዳይ ለመከታተል ወደ ፍርድ ቤት በመምጣታቸው ጉዳያቸው በግልጽ ችሎት መታየት ይገባው የነበረ ቢሆንም በቢሮ በኩል ጉዳያቸው እንዲታይ ተደርጓል፡፡

የአንድነት አባላትን ጉዳይ ይመለከቱ የነበሩት ዳኛ ማሞ ሞገስ ተቀይረው ዳኛ ሬድዋን ጀማል ተሰይመዋል፣ የዛሬው ቀጠሮ ፖሊስ ቀረኝ የሚለውን ምርመራ አጠናክሮ እንዲያቀርብ ካልሆነም በነጻ እንዲሰናበቱ ለመወሰን የነበረ ቢሆንም ‹‹ተጠርጣሪዎቹ አመጽ ለማስነሳት በማቀድ ወረቀት በትነዋል›› የሚለውን ክሱን የሚያስረዳ ማስረጃ ሊያቀርብ አልቻለም፡፡ተጠርጣሪዎቹ ‹ለሰላማዊ ሰልፉ እውቅና መስጠት ይገባው የነበረ አካል በመዘግየቱ እንጂ ወረቀት መበተናችን ህገ ወጥ አያሰኘንም› በማለት ከክሱ በነጻ እንዲሰናበቱ ጠይቀዋል፡፡ዳኛው በስተመጨረሻ እያንዳንዳቸው አንድ ሺህ ብርና የመንግስት ሰራተኛ በዋስትና እንዲያቀርቡ በማዘዝ ፋይሉን ወደ መዝገብ ቤት እንዲመለስ አድርገዋል፡፡

ገንዘብ በዋስትና እንዲያቀርቡ ከተጠየቁ በኋላ የመንግስት ሰራተኛ በዋስትናው ላይ እንዲጨመር መደረጉም አስገራሚ እንደሆነ በስፍራው የነበሩ አባላት ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡የተቃዋሚ ፓርቲ አባል የሆነ ሰው ሲታሰር የመንግስት ሰራተኛ ዋስ እሆናለሁ ቢል ከስራው ሊያፈናቅሉት እንደሚችሉ ስለሚገምት፣ ለተቃዋሚዎች የመንግስት ሰራተኛን ዋስ አድርጎ የጠየቀዉን ፍርድ ቤቱ እንዲለውጥ፣ የፓርቲው አመራሮች ለዕለቱ ዳኛ አቤት ብለዋል፡፡

 

ሐሙስ ሚያዚያ 2 ቀን  2006 ዓ.

ዳኛው የአንድነት አመራር አባላትን ጥያቄ አልተቀበለም። እስረኞቹ  አንድ ሺህ ብር ከፍለው፣ የመንግስት ሰራተኛ ዋስ አቅርበው ይፈታሉ። እስረኞቹ የደረሰባቸው ነገር ወደ ኋላ እንደማይጎትታቸው፣ ትግሉን የበለጠ እንደሚያጠናክሩ ይናገራሉ።

ኬንያ ያሉ ስደተኞች ብሦት ቀጥሏል (VOA)

$
0
0

ኬንያ በስደተኞች ላይ እያካሄደች ነው የሚባለው የአፈሣ እና የማሠር እርምጃ እስከትናንት ምሽት መቀጠሉ ተነግሯል፡፡

ኬንያ በስደተኞች ላይ እያካሄደች ነው የሚባለው የአፈሣ እና የማሠር እርምጃ እስከትናንት ምሽት መቀጠሉ ተነግሯል፡፡ትናንትናና ዛሬ ወደ 55 ኢትዮጵያዊያንና ከ86 እስከ 90 የሚሆኑ ሶማሊያዊያን ስደተኞች ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ መደረጉን ስደተኞቸ አመልክተዋል፡፡ለቪኦኤ ያሉበትን ሁኔታ የተናገሩ ሰዎች እርምጃው አግባብነት የሌለውና ሥርዓትን የጠበቀ አይደለም ይላሉ፡፡በሌላ በኩል ደግሞ “ሕገወጥ ፍልሰተኞች አሉ” በሚል ሰበብ ፖሊስ አፈሣውን ተገን አድርጎ ጉቦ እየተቀበለና እያንገላታታቸው መሆኑን እዚያ የሚገኙ የሶማሊያ ስደተኞች ለዘጋቢያችን ጌብ ጃሰሎ ነግረውታል፡፡የኬንያ ፖሊስ ደግሞ ስለጉቦው ከጭምጭምታና ከሐሜት በስተቀር በይፋ የቀረበልኝ ክስ የለም ብሏል – ለቪኦኤ፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

 

VOA 1

 

አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ ቁጥር 5 – PDF ከአዲስ አበባ

$
0
0

afro times (1)_Page_01
አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ በታወቁ የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኞች የምትታተም ነፃና የግል ጋዜጣ ናት። የጋዜጣዋ ፒዲኤፍ እንደደረሰን ሁሌ በዘ-ሐበሻ ድረገጽ ለማንስነበብ እንሞክራለን። ለዛሬው፦
ሙሉውን መጽሔት ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

አባይን ለመንከባከብ የጎሰኛነት አገዛዝ በዲሞክራሳዊ አገዛዝ መተካት አለበት አክሎግ ቢራራ (ዶር)

$
0
0
Dr. Aklog Birara

Dr. Aklog Birara

“ለምንወደው ለዛሬው ሕዝባችንም ሆነ፤ ከዘመን ወደ ዘመን ለሚከተለው ትውልድም ጭምር፤ የዓባይን የውሃ ሃብት ለሕይወቱ  ደህንነትና ለፍላጎቱ ማርኪያ እንዲውል ማድረግ፤ ኢትዮጵያ ከፍ ያለ ግምት የምትሰጠውና በቅድሚያ የሚያሳስባት ጉዳይ ነው።  አምላካችን ያበረከተላትን ይህን ሃብቷን ለሕዝባቸው ህይወትና ደህንነት በማዋል እንዲጠቀሙበት ከጎረቤት ወዳጅ አገሮች ጋር  በለጋስነት በጋራ ለመካፈል ዝግጁ ብንሆንም፤ ይህን የውሃ ንብረቷን በቁጥር እየጨመረ ለሚሄደው ሕዝቧና በማደግ ላይ ላለው  ኢኮኖሚ ጥቅም እንዲውል ማድረግ የኢትዮጵያ ተቀዳሚና የተቀደሰ ግዴታዋ ነው።”

ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

አዎ ማኅበረ ቅዱሳንን ተጠንቀቁ ! ትልቁ ስጋት እሱ ነውና አዲሱ ተስፋዬ

$
0
0

አዲሱ ተስፋዬ

 መነሻ

snaplvrይህንን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ሰንደቅ ጋዜጣ በሚያዝያ 1/2006 ዓ.ም እትሙ ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ያወጣው ቃለ መጠይቅና ሀተታ ነው [i] :: ሶስቱም አስተያየት ሰጭዎች “ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ነው:: ስለዚህም መንግስት ሊያፈርሰው ነው ” የሚለው ወቅታዊ ዜና ምንጩ ከየት እንደሆነ ግልጽ እንዳልሆነ ጠቅሰዋል :: በፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አበበ ወርቁ ጉዳዩን “በሬ ወለደ ነው” ብለው ሲያጣጥሉት ፣ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ደግሞ ” የዚህ ወሬ ምንጩ ከየት እንደሆነ አናውቅም” ሲሉ ተመሳሳይ ነገር ተናግረዋል።

ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው እንዴ?

በ 1955 እ. ኤ. አ የተመሰረተውና መቀመጫውን በኔዘርላድና በዩናይትድ ስቴትስ ያደረገው  Open Doors : Serving Persecuted Christians Worldwide [ii] የተሰኘው ግዙፍ ድርጅት 2013 እ. ኤ. ኣ ባወጣው World Watch List ላይ ክርስትያኖችን በማሰቃየት በ63 ነጥብ ኢትዮጵያ 15ተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝና ፣ ለዚህም ስቃይ ዋና ተዋናይ ከሆኑት አካላት አንዱ ማኅበረ ቅዱሳን እንደሆነ ጽፎ ፣ ሊስቱንም በመላው ዓለም በትኗል [iii] ። ይሄው በመላው ዓለም በድረ ገጽና በተለያዩ ኤለክትሮኒክ ሚድያዎች (hard and soft copy) የተበተነው ሪፖርት ከመስክ የመረጃ ሰራተኞቼ ፣ ከምሁራንና ከሰላዮቼ አገኘሁ ባለው መረጃ መሰረት አቶ መለስ ዜናዊን ሞት ቀደማቸው እንዲ ማኅበረ ቅዱሳንን እንክትክቱን ሊያወጡት አቅደው እንደነበረ ፣ ቀጣዩም ግዜ ማኅበረ ቅዱሳን የሚገንበት ግዜ እንደሚሆንና ይሄም ለተሐድሶዎች አስቸጋሪ ግዜ ስለሚሆን ከማኅበረ ቅዱሳንን እንዲጠበቁ እንዲህ በማለት ያትታል

“The death of Prime Minister Meles Zenawi, who sought to crush Mahibere

Kidusan, the fanatical group inside EOC, is considered a big blow for the renewal movements. Zenawi was not a supporter of those movements, but his actions against Mahibere Kidusan for political survival were considered by the EOC renewal movements as helpful for less squeeze. His replacement, Haile Mariam Desalegn, does not possess the political and religious background required to confront the fanatical group. Mahibere Kidusan is currently riding high and…. In addition to this, the death of the EOC leader is a big shock for the renewal movements as he was reluctant to take action against them. “ [iv]

ይሄው ዓለማቀፋዊ “የክርስትያኖች እንባ ጠባቂ” ነኝ የሚለው ድርጅት ማኅበረ ቅዱሳን በመንግስት የደህንነት መዋቅር ውስጥ ዘልቆ እንደገባና የመንግስትን ስልጣን በመቆጣጠር በተለይ “የተሐድሶን ቡድን ” ለማጥፋት መነሳቱን በዚህ መልኩ ሪፖርቱ ላይ ገልጾታል

(MK) normally monitor the churches. The fanatic group inside the EOC (Mahibere Kidusan) has to be mentioned here. Particularly Open Door Field experts report that the group is now a growing threat for non-traditional protestant churches and renewal movements with in the EOC. The group ( MK) allegedly has an ambition to influence and control the government policies to restrict the activities of other religions. There are reports that Mahibere Kidusan has managed to infiltrate the government security and administrative apparatus. In the absence of a powerful leader and the death of a relatively moderate patriarch (late leader of EOC) the next move of the group is nervously watched.[v]

እስካሁም “ያዋጣናል ፤ ማኅበሩን ለመምታት ጥሩ መላ ነው”  ብለው ያሴሩት “ማኅበሩ አስራት ይወስዳል፣ ግብር አይከፍልም ፣ ሕንጻ ገንብቷል ወዘተ” የሚል ነበር። ማኅበሩ አስራት እንደማይወስድ ፣ ሂሳቡንም በተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያዎች ኦዲት በማስደረጉና ከግብርና መሰል ክፍተቶች የጸዳ መሆኑን በማረጋገጡና የውንጀላ ክፍተት በመጥፋቱ ሌላ ዜማ ጀምረዋል። አሁን ደሞ ክሱ “ማኅበሩ መንግስት ደህንነት መዋቅር ውስጥ ገብቶ ሊያፈርሰን ነው” የሚል ሆኗል።ይሄም እንደማያዋጣ ያወቁት እኩያን አሁን ደሞ የመጨረሻ ጥይታቸው ተቀይሯል። ማኅበሩ ፖላቲካ ውስጥ ገብቷል እና መንግስት ወዮልህ አይነት ዝባዝንኬ።

 

እናም  ማኅበረ ቅዱሳንን ተጠንቀቁ !

ይሄው ሪፖርት  ኦርቶዶክሳዊት ቅድስት ቤተ ክርስትያን ውስጥ ገብተው፣ ቤተ ክርስትያንን እየገዘገዙ ላሉ ራሳቸውን ተሐድሶ ብለው ለሰየሙ ውስጠ ተኩላ ወገኖቹ ያስተላለፈው ጥሪ አንድ ነው :: ” አክራሪው ማኅበረ ቅዱሳንን እየበረታና እየጠነከረ ስለሄደ የሚቀጥሉት አመታት ለተሐድሶዎች እጅግ አስቸጋሪ ነውና … ማኅበረ ቅዱሳንን ነቅታችሁ ጠብቁ:: ከዚህም ስጋት የመነጨ ይመስላል ግብረ አበሮቻቸው ማኅበረ ቅዱሳንን ለማወክ ያለ የሌለ ሃይላቸውን አስተባብረው መንጫጫት ከጀመሩ ሰነባተዋል

Now, in his absence and with the government’s reduced leverage, this fanatic group ( Mahibere Kidusan) appears to be taking charge. The coming months may bring difficult times for the renewal movements inside the EOC…the next move of the group is nervously watched.[vi]

ይሄ ድርጅት መንደርተኞች የፈጠሩት የሰፈር እቁብ አይደለም:: በመላው ዓለም ኔት ወርክ ያለው መሰረተ ሰፊ ድርጅት ነው:: የሚያወጣቸውንም ሪፖርቶች ሚሊዮኖች ያነቡታል:: የኢትዮጵያ “ክርስትያኖችን ዋይታ” በተመለከተ ያወጣው ጽሁፍ ግን ይገርማል:: ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ክርትስትያኖች ተገድለዋል:: ተሳደዋል:: አብያተ ክርስትያናትም ተቃጥለዋል:: ገዳማትም ተደፍረዋል:: ክርስትና ለሚገደው አካል እነዚህ ብዙ የሚያስጽፉ ነበሩ:: ይሄ ሪፖርት ግን ያተኮረው ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ነው:: የማኅበሩም ወንጀሎች ብሎ ሊነገረን የሚፈልገው አንድ ነገር ” ማኅበረ ቅዱሳንን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያንን ትምህርትና ዶግማ አፍርሰው ወደ ሌላ እምነት ድርጅት ለመቀየር የተነሱ ተሐድሶዎችን አላስቀምጥ አለ:: ለተሐድሶ እንቅስቃሴ እንቅፋት ሆነብን “ የሚል ነው:: እንግዲህ የማኅበሩ ወንጀል ይሄ ነው:: ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር የተናገሩትንም አስተያየት ጠምዝዞ ” ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ሞት ቀደማቸው እንጂ ሊያፈራርሱት ነበር” በማለት እውነቱን ሳይሆን ምኞቱን ተርኮልናል:: የሚገርመው ” ማኅበረ ቅዱሳንን በማፍስ ሂደት ጉልህ ሚና አልተጫወቱምና ተተኪው ጠቅላይ ሚኒትር አቶ ኃይለማርያምን “አቅም ያነሳቸው” እስከማለት ደፍሯል:: ፓትርያርክ ጳውሎስንም ” ተሐድሶ ላይ እጃቸውን ማንሳት የማይፈልጉ ለዘብተኛ” ሲል አሞግሷቸዋል:: እንደዚህ ድርጅት ዘገባ ቤተ ክርስትያንን ለመሰርሰር ሰርገው የገቡ መናፍቃን ሰማዕታት ሲሆኑ፣ የአባቶቼን ርስት አልሰጥህም በሚል ለቤተክርስትያን ትውፊትና እምነት መጠበቅ የሚደክመውን ማኅበረ ቅዱሳንን ደግሞ አሸባሪ ፣አክራሪ የሚል የስም ጥላሸት እንዲቀባ ተደርጓል:: እንግዲህ የማህበረ ቅዱሳን ወንጀሉ ይሄ ነው::

 

 

ማኅበረ ቅዱሳን ወሳኝ ሃይል ሆኗል

 

ከቅርብ ግዜ ወዲህ ማኅበረ ቅዱሳንን በአክራሪነትና በነውጠኛነት የመፈረጁ አባዜ በአካዳሚክ ጽሁፎች ላይም እየታየ ነው :: ለምሳሌ የዶክተር ጥበበ እሸቴን የዶክትሬት ማሟያ ጽሁፍ ማንሳት ይቻላል:: ዶክተር ጥበበ በ 1960ዎቹ ውስጥ በነበረው የተማሪዎች እንቅስቃሴ ተሳትፎ የበራቸው እና በኋላ ደግሞ የፕሮቴስታንቱን ዓለም በመቀላቀል በዛው ድርጅት ውስጥ የአስተዳደር ቦታ እስከመያዝ የደረሱ ሰው ናቸው:: እኚህ ሰው 2009 ላይ The Evangelical Movement in Ethiopia : Resistance and Resilience በሚል ርዕስ የጻፉትን የዶክትሬት ሟሟያ ጽሁፋቸውን አሳትመዋል[vii]:: በዚህ አወዛጋቢ መጽሐፍ ዶክተር ጥበበ ማህበረ ቅዱሳንን militant, aggressive, anti evangelical በማለት ጥላሸት በመቀባት አንባቢን የሚያደናግር አንቀጽ አስፍረዋል:: ያይጥ ምስክሯ ድንቢጥ ነው ነገሩ::

 

The emergence of a highly aggressive and more militant movement that arose with in the Orthodox Church under the name of Mahibere Kidusan in recent years should be seen in multidiscrusive context…     (Mahibere Kidusan) as a nationalistic and strongly anti-evangelical movement enjoying the backing of some orthodox conservative intellectuals and elements of the urban youth , the new religious strain is becoming a significant force [viii]

 

ዶክተር ጥበበ ለምን ዓላማና በምን መረጃ militant ( ነውጠኛ) anti evangelical (ጸረ ወንጌል) እሰከማለት እንደደረሱ ባላውቅም እሳቸውም ግን ገና በ2009 ማኅበረ ቅዱሳን significant force ሆኖዋልና አስቡበት ሲሉ አስገንዝበው ነበር:: ምንም እንኳን ዶክተር ጥበበ እሸቴ በዚህ ጥናታዊ ጽሁፋቸው ላይ በርካታ አመኔታ የሚጎድላቸው ነጥቦችን ቢያስነብቡንም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን ውስጥ፣ ቤተክርትስያኗን ወደ ሌላ እምነት ድርጅት ለመቀየር በስውር የሚሰሩ የተጠናከሩ ህቡዕ ቡድኖች እንዳሉና ተጽኗቸውም በሰንበት ትምህርት ቤቶች፣ በየማህበራቱ ፣ በየአጥቢያ ቤተክርትያንቱ እንዲሁም ገዳማቱን ሳይቀር መታየት መጀመሩን የውስጥ አዋቂ በሚመስል ሁኔታ እንዲህ በማለት ገልጸውታል::

 

Today, many underground movements are operating with in Ethiopian Orthodox Church, some with evangelical and others with Pentecostal convictions. ..Some of these movements exemplify attempts at religious innovation, though it is hard to plot their trajectories because of their hidden nature and complex character. Such developments are affecting wide ranging areas of the established structure of the Orthodox institutions, such as Sunday Schools, the mahibers, the monastic centers, and even the local churches in major cities. [ix]

 

የፕሮቴስታንቱ ዓለም ፓስተሮችም ከ34,000 የማያንሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርትያናት ውስጥ ገብተው ቤተ ክርስትያኗን ወደ ፕሮቴስታንቱ ዓለም ለመገልበጥ አባላትን እየመለመሉና ስልጠና እየሰጡ እንደሆነ በጀብዱ መልክ በአደባባይ እየተናገሩ ነው::

The evangelist is hopeful that the seeds of revival are being planted and nurtured in the estimated 34,000 Orthodox churches in Ethiopia and abroad. So far more than 600 people have successfully completed the two-week course.[x]

 

አልፎ ተርፎም ማኅበረ ቅዱሳንን ባይኖር የተሐድሶ እንቅስቃሴ ቤተክርትያኗን ሙሉ ለሙሉ ይቆጣጣራት እንደነበር በይፋ እየተጻፉ ነው:: ማኅበረ ቅዱሳንም ላይ ጥርሳቸውን የሚያገጫግጩት ለዚህ እኩይ ዓላማቸው እንቅፋት ስለሆነባቸው ነው ።ለዚህም ዓላማቸው ስኬት ማኅበረ ቅዱሳንን ሊያፈስርና ሊበትን የሚችል ዘርፈ ብዙ ስራ በመስራት ላይ ይገኛሉ:: ቤተ ክህነቱ ውስጥ በገንዘብ የገዟቸው ቅጥረኞቻቸው ማኅበሩን ለማፍረስ የቻሉትን ያህል ሄደዋል::

 

ግን ከኪሳራ ውጭ ማኅበሩ ላይ ምንም ያመጣው ጉዳት አለመኖሩ ያሳሰባቸው አካላት አሁን ደግሞ ቤተ ክህነቱ ውስጥ ሰግስገው ላስገቧቸው ቅጥረኞቻቸውና በገንዘብ ለገዟቸው ይሁዳዎች የመጨረሻ ትንቅንቅ እንዲያደርጉ እንደላኳቸው በየቀኑ የምናየው ሃቅ እየሆነ ነው::

 

ዝነኛው ጋዜጠኛ ተመስገን ዘውዴ የማኅበረ ቅዱሳን የመጨረሻዎቹ ቀናት በሚል ርዕስ በቅርቡ ባስነበበን ግሩም ጽሁፍ ላይም የማኅበሩ ተቃዋሚዎች ቤተ ክህነት ውስጥ አዳራሽ ተፈቅዶላቸው ማድረጋቸውንና የአቋም መግለጫ እስከማውጣት መድረሳቸውን እንዲህ ሲል ነበር ያስነበበን

 

ለመጽሔቱ ዝግጅት ክፍል የደረሰው በድምፅ የተቀረፀ የውይይቱ ሙሉ ክፍል እንደሚያስረዳው፣ ተሰብሳቢዎቹ ማኅበሩን በተመለከተ ያወጡት የአቋም መግለጫ÷ የማኅበሩና የዋነኛ መሥራቾችና አባላት የባንክ አካውንት፣ ቀላልና ከባድ ተሸከርካሪዎች ጨምሮ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረቶች፣ ት/ቤቶች፣ የንግድ ተቋማት፣ የአክስዮን ተቋማት፣ የንዋያተ ቅድሳት ማምረቻዎችና ማከፋፈያዎች፣ ከቀረጥ ነጻ የገቡና በመግባት ላይ ያሉ ዕቃዎች በሚመለከታቸው የመንግሥት መሥ/ቤቶች እንዲታገዱ በቅ/ሲኖዶስ አማካይነት ደብዳቤ እንዲጻፍ፤ ከምእመናን በቀጥታም ኾነ በተዘዋዋሪ የሚቀበለው ዓሥራት እየፈረጠመበት ስለኾነ እንዳይቀበል ይከልከል፤ የግቢ ጉባኤያት(የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) እርሱ በሚቀርፀው ትምህርት እንዳይወሰዱብን በደንብ መሥራት፤ ተጠሪነቱ ከዋና ሥራ አስኪያጅነቱ ሥር ወጥቶ በሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ውስጥ አንድ ንኡስ ክፍል ይኹን የሚሉና የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡[xi]

 

ይሄን የአቋም መግለጫ ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው የተሰብሳቢዎቹ አንዱና ዋና እቅድ የግቢ ጉባኤያት(የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) እርሱ በሚቀርፀው ትምህርት እንዳይወሰዱብን በደንብ መሥራት፤የሚል ነው። ማኅበረ ቅዱሳን ለየግቢ ጉባ ኤያት ቀርጾ ያዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት እና መመርያ መጻሕፍቱ በሙሉ ይታወቃሉ። ቢጋሮቹም ፣ መጻሕፍቱም በሊቃውንቱ ታይተው የተመረመሩና የታረሙ ፍጹም ኦርቶዶክሳዊ ናቸው። እርሱ በሚቀርጸው ትምህርት እንዳይወሰዱብን ማለት ትርጉሙ ምንድነው? ይሄ እንግዲህ እየተካሄደ ያለው ቤተ ክህነት አፍንጫ ና ብብት ስር ነው።

 

ማኅበረ ቅዱሳን የኔ ነው ! ያንተ ነው!  ያንቺ ነው! የኛ ነው!

 

ምንም እንኳን ቤተ ክርስትያን ከፈተና ተለይታ ባታውቅም ቅድስት ቤተ ክርስትያናችን አሳሳቢ ፈተና ውስጥ ወድቃለች። ከአውሮፓና አሜሪካ ድረስ ሳይቀር ድርጎ የሚታሰብላቸው ሆድ አምላኪዎች የቤተ ክርስትያንን አባቶችን ክብር በማጉደፍ፣ የቤተ ክርስትያንን ትውፊትና ትምህርት በመገዝገዝ፣ ቤተ ክርስትያንን ወደ መናፍቃኑ ጎራ ለማስረከብ ሌት ተቀን እየሰሩ ይገኛሉ። በተለይም ራሳቸውን ተሐድሶ በሚል የሰየሙ ቡድኖች ቤተ ክርስትያኗን ለማፍረስ ቆርጠው ተነስተዋል። ለዚሁ እኩይ ዓላማቸው መሳካት ማኅበረ ቅዱሳን እንቅፋት ስለሆነባቸው ከምሁር እስከ ተርታው አባል ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ዘመቻ ከፍተዋል። የማኅበሩን ስም ለማጥፋት በርካታ ብሎጎች ሥራ ላይ ውለዋል። ብዙ ብር ወጥቶባቸው መጻሕፍት ታትመዋል።ህሊናቸውንና ሃይማኖታቸውን በብር በሸጡ ይሁዳ የቤተ ክህነት ሰዎችም ማኅበሩን ለመምታት ዘርፈ ብዙ ሙከራ ተደርጓል። አንዱም ማኅበሩን ለማፍረስ አቅም ባይኖረውም።አረቦቹ እንደሚተርቱት ውሾቹ ይጮሃሉ።ግመሉ ግን ይጓዛል።

 

እኛስ ለሃይማኖታችን የሚገደን ኦርቶክሳውያንስ ምን እያደረግን ነው? ማኅበረ ቅዱሳን የቤተክርስትያን እጅ ነው[xii]። የቤተ ክርስትያን አካል ነው።ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር የሚደረግ ትግል ሁሉ ቤተ ክርስትያንን ለመጣል የሚደረግ ሰይጣናዊ ትግል ነው። ማኅበረ ቅዱሳን ላይ የሚታወጅ ጦርነት በሙሉ ቤተ ክርትያን ላይ የተቃጣ ጥቃት ነው ።ማኀበረ ቅዱሳንንም ኢላማ ውስጥ እንዲገባ ያደረገው ዋነኛ ምክንያት፣ ይሄ ትውልድ ስለ ኦርቶክሳዊ ማንነቱ የላቀ ግንዛቤ እንዲኖረው ማስተማሩና ከቤተ ክርስትያን ጎን መቆሙ ነው ። የማኅበረ ቅዱሳን ጥንካሬ የቤተ ክርስትያን ጥንካሬ ነው። ማኅበረ ቅዱሳን ላይ የሚቀሰሩ ጣቶች በሙሉ ቤተ ክርስትያን ላይ የሚቀሰሩ ጣቶች ናቸው ።ስለዚህ ማኅበሩ ላይ የሚደረጉ ትንኮሳዎች ቤተ ክርስትያን ላይ እይሚደረጉ ትንኮሳዎች ናቸውና እያንዳንዳችን ኦርቶዶክሳውያን ቆመን ማሰብ አለብን አለብን።

 

ማኅበረ ቅዱሳን ይፈርሳል እንዴ ?

 

“ማኅበረ ቅዱሳን ይፈርሳል” ብለው ለሚቃዡ ሰዎችም እውነታውን አውቀውት ከወዲሁ እርማቸውን እንዲያወጡ ትንሽ ልበል። ዛሬ እኮ የትኛውም ዓለም ብትሄድ የማኅበረ ቅዱሳን ሴል (Cell)  የሌለበት ክፍለ ዓለም የለም።ኢትዮጵያ ውስጥ እያንዳንዱ ቀበሌ ድረስ ” እምቢ ለቤተክርስትያኔ” የሚሉ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት አሉልህ።ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ እያንዳንዱ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ ለቤተ ክርስትያን ሁለንተናዊ እድገት ነቅተው የሚሰሩ የማኅበሩ አባላት አሉ ። የማኅበሩ መመርያ እንደሚያዘው እያንዳንዱ የማኅበር አባል የሰንበት ትምህርት ቤት አባል ነው። የትኛውም ቤተ ክርስትያን ሰበካ ጉባኤ ውስጥ ቤ ክርስትያንን ባላቸው አቅም ለማገልገል ቁርጥ አቋም ያላቸው የማኅበሩ አባላት አሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ የትኛውም የመንግስትም ሆነ የግል ድርጅት ውስጥ የማኅበሩ አባል የሌለበት የለም ። እያንዳንዱ መስሪያ ቤት ያለ ተቀጣሪ የማኅበረ ቅዱሳን ተጽዕኖና አሻራ የሌለበት የለም ። የማኅበሩ ቋሚ አባል ባይሆን እንኳን የማኅበሩ ግን ሙሉ ደጋፊ ነው ።ወይም በዘመኑ ቋንቋ ስትፍቀው ማኅበረ ቅዱሳናዊ ነውማኅበረ ቅዱሳን በየቀኑ ለቤተክርትስያንን ጉዳይ የሚንገበገብ ፣  የሚያስብ ትውልድ ፈጥሯል።ይህ ትውልድ ማኅበረ ቅዱሳናዊ ነው። ቢመረንም ፤ቢዋጠንም።

 

ከኢትዮጵያም ውጭ የማኅበሩ ቅርንጫፍ የሌለበት ቦታ የለም። በተለይ በሰሜን አሜሪካ እና አውሮፓ ። ዛሬ ዛሬ በሰሜን አሜሪካና በአውሮፓ የሚደረጉ የማኅበሩ ጠቅላላ ጉባኤያት ከሀገር ውስጡ የማይተናነሱ እየሆኑ ነው። በዓረቡ ዓለምና በዕሥያ ያለው የማኅበሩ እድገትም ቀላል አይደለም። የትኛውም ክፍለ ዓለም ላይ የቤተ ክርስትያን ጉዳይ የሚገደው በቤተ ክርስትያን ጉዳይ ዝም የማይል የማኅበረ ቅዱሳን ሕዋስ አለ። ባጭሩ ማኅበሩ global ሆኗል። ወይ ደግሞ ነፋስ ሆኗል።አትይዘው አትጨብጠው። ነፋስ የማይነፍስበት ቦታ እንደሌለ ሁሉ ማኅበሩ የሌለበት ቦታ የለም።ማን ነበር ማኅበረ ቅዱሳን የሃሳብ መስመር ( Imaginary line) ሆኗል ያለው። ማኅበረ ቅዱሳንን ልዝጋው ብሎ የሚያስብ አላዊ እንኳን ቢመጣ አዲስ አበባና በየዞኑ ያለውን ጽፈት ቤት ሊዘጋ ይችል ይሆናል።ማኅበረ ቅዱሳንን ማጥፋት አይችልም::  ዋናው የማኅበሩ ሥራ የሚሰራው በያንዳንዷ ደብር ፣ በየሰበካ ጉባኤው ፣ በየሰንበት ትቤቱ ፣ በየ አባላቱ ቤት ስለሆነ ማኅበረ ቅዱሳን ላይ የሚያመጣው ለውጥ insignificant ነው። ሰሜን አሜሪካ ያለው ማዕከል ብቻውን አዲስ አበባ ያለው ማስተባበርያ የሚሰራውን ሥራ የምስራት አቅም አለው። እድሜ ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዛሬ አሜሪካ ሆነህ በያንዳንዱ ቀበሌ ፣በያንዳንዱ አጥቢያ ያለውን አባል ለቤተ ክርስትያን ሥራ ማስተባበር ከባድ አይደለም። It is a click or one call away. ማኅበሩ በአንድ የጸሎት ቋንቋ የሚናገሩ ፣ በአንድ የእምነት ልብ የሚመሩ ፤ እንደ አንድ ቃል ተናገሪ እንደ አንድ ልብ መስካሪ የሆኑ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኦርቶክሳውያን ስብስብ ነውና እንዲህ በቀላሉ እንደ አንቧይ ካብ አትንደውም።ብትሰረስረውም መሰረቱ ጠንካራ አለት ነውና አታፈርሰውም። ከሁሉም በላይ የማኅበሩ ጠባቂ እመብርሃን ናትና ገና ይሄ ማኅበር ያድጋል። ይሰፋል።

ማስገንዘቢያ

ይህ ጽሁፍ የኔ የራሴ የግል ምልከታዬ እንጂ ሌላ ማንንም አይወክልም:: አስተያየት ሊሰጡኝ ከወደዱ በዚህ ኢ ሜይል ይላኩልኝ

redawube@gmail.com

 

 

 



[i] http://www.sendeknewspaper.com/images/Sendek-Pics/448/448.pdf

[iii] http://www.opendoors.no/vedlegg/1988472/WWL2013-FullReport-en

[v]  ibid

 

[vi] Ibid

[vii]  Eshete,Tibebe  The Evangelical Movement in Ethiopia : Resistance and Resilience 2009 Bayor University press

[viii]  Ibid ( page 313)

[ix] Ibid ( page 61)

[x] http://www.charismamag.com/blogs/189-j15/features/africa/530-revival-and-persecution-in-ethiopia

[xi] ፋክት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፴፱፤ መጋቢት ፳፻፮ ዓ.ም.

የኢቲቪ “የቀለም አብዮት”ስጋት!

$
0
0

አብርሃ ደስታ

Abrha Destaኢቲቪ “የቀለም አብዮት” ዝግጅት (ስጋት) አቀረበልን። ግን የኢህአዴጉ ኢቲቪ ለምን የቀለም አብዮት ጉዳይ አጀንዳ አደረገው? የቀለም አብዮት ጉዳይ ለምን ዝግጅት አስፈለገው? አዎ! “የቀለም አብዮት” ጉዳይ አጀንዳ የሆነው የቀለም አብዮት (በትክክለኛው አጠራሩ ህዝባዊ ዓመፅ) ስጋት ስላለ ነው። የህዝብ ዓመፅ (የቀለም አብዮት) ለምን ስጋት ሆነ? ኢህአዴግ ለምን ህዝባዊ ዓመፅን ሰጋ? ተግባሩ ስለሚያውቅ ነው።

የኢህአዴግ መንግስት ዓፋኝ መሆኑ አውቀዋል፣ ተገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ዓፈና እንደማያስፈልገው መገንዘቡም የኢህአዴግ መንግስት የተገነዘበ ይመስለኛል። ህዝብ ስለ ዓፈና ግንዛቤ ካለው ነፃነት መፈለጉ አይቀርም። ነፃነት የፈለገ ህዝብ በማፈን መግዛት እንደማይቻል ኢህአዴጎችም የተገነዘቡት ይመስላል።

አሁን ኢህአዴግ የህዝብ ድጋፍ እንደሌለው እየተረዳ ነው። የኢህአዴግ ዓላማ ስልጣን እስከሆነ ድረስ በህዝብ ባይመረጥም የህዝብን ድምፅ አጭበርብሮ የተመረጠ አስመስሎ በስልጣን ለመቆየት ጥረት ማድረጉ አይቀርም። ነፃነት የፈለገ ጭቁን ህዝብ ድምፁን ለማስከበር ጥረት ሲያደርግ የህዝብ የነፃነት ትግል ከኢህአዴግ የስልጣን ፍላጎት ጋር ይጋጫል። ግጭቱ ህዝባዊ ዓመፅ ሊወልድ ይችላል የሚል ስጋት አድሮበታል። ለዚህም ነው የቀለም አብዮት (ህዝባዊ ዓምፅን) አጀንዳ አድርጎ ዝግጅቱ (ይቅርታ ስጋቱ) ያቀረበልን።

በኢቲቪ ከቀረበልን ዝግጅት በመነሳት ኢትዮጵያ የቀለም አብዮት (ህዝባዊ ዓመፅ) ያሰጋታል። ምክንያቱም የኢህአዴግ መንግስት ህዝባዊ ዓምፅን ባያሰጋው (ባይፈራ) ኑሮ በምስራቅ አውሮፓና ላቲን አሜሪካ ስለተከናወኑ የቀለም አብዮቶች ባላሳሰበው ነበር። ኢቲቪዎች “ምዕራባውያን የራሳቸው ጥቅም ለማሳካት ሲሉ በሌሎች ሀገሮች ህዝባዊ ዓመፅ እንዲቀሰቀስ ያደርጋሉ” አሉን። በዓለም አቀፍ ግኑኝነት ማንኛውም ሀገር የራሱ ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር ይሰራል። ምዕራባውያን ይሁኑ ምስራቃውያን የየራሳቸው ጥቅም ለማስከበር ነው የሚሰሩት። ይህ ግልፅ ነው።

ዓቅም ያላቸው ሐያላን ሀገራት በአንድ ሀገር የመንግስት ግልበጣ ሊያካሂዱ ይችላሉ (በገንዘብና በወታደራዊ ሃይል በመታገዝ)። የዉጭ ሃይል መፈንቅለ መንግስት ሊያካሂድ ይችላል። ህዝባዊ ዓመፅ የመቀስቀስ ዕድሉ ግን አነስተኛ ነው። ምክንያቱም ህዝባዊ ዓመፅ የሚካሄደው በሀገርኛ ህዝብ ነው። የዉጭ ሀገር መንግስት ብጥብጥ ወይ ዓመፅ ሊቀሰቅስ ይችላል። ዓመፁ የሚካሄደው ግን በህዝብ ነው። ስለዚህ የህዝባዊ ዓመፅ ዋነኛ ተዋናይ ህዝብ እስከሆነ ድረስ የዉጭ ሃይል ዓመፅ የመቀስቀስ እንጂ ዓመፅ የማካሄድ ዕድል የለውም። ምክንያቱም የዉጭ ሃይል ፍላጎቱ ለማሳካት ዓመፅ ቢቀሰቅስ እንኳ ህዝቡ ቅሬታ ከሌለው፣ ነፃነቱ ከተጠበቀ፣ ካልታፈነ ለዓመፅ አይዘጋጅም። ህዝብ ለዓመፅ ካልተዘጋጀ የዉጭው ሃይል የፈለገ ጥረት ቢያደርግ አይሳካለትም።

በአንድ ሀገር ህዝባዊ ዓመፅ ሊቀሰቀስ የሚችለው በዉጭ ሃይል ፍላጎት ሳይሆን በጭቆና ነው። ህዝብ ሲጨቆን ነፃነት ይፈልጋል። ነፃነት ሲፈልግ ከስልጣን ጥማተኛ አምባገነኖች ጋር ይጋጫል። አምባገነኖች የህዝብን የነፃነት ጥያቄ በሃይል ለመጨፍለቅ ይሞክራሉ። ህዝብ ያምፃል። ህዝባዊ ዓመፅ ይቀሰቀሳል። ስለዚህ የህዝባዊ ዓመፅ መንስኤ ጭቆና ነው። ህዝብ የስልጣን ባለቤት ከሆነ፣ ዴሞክራሲያዊ መብቱ ከተጠበቀለት፣ በእኩል ዓይን ከታየ፣ ፍትሕ ከሰፈነ ወደ ዓመፅ የሚሄድበት ምክንያት አይኖርም።

ኢህአዴጎች “የቀለም አብዮት” ከምዕራባውያን ብሄራዊ ጥቅም ጋር ያገናኙበት ምክንያት ምናልባት ኢትዮጵያ ዉስጥ ህዝባዊ ዓመፅ ቢቀሰቀስ ‘የኢትዮጵያውያን ቅሬታ የቀሰቀሰው ሳይሆን የምዕራባውያን ሴራ ነው’ በማለት ዓመፁ በሃይል ለመጨፍለቅ እንዲችሉ ሐሳባዊ ቅድመ ዝግጅት ለማስቀመጥ ነው። ግን እስካሁን የተደረጉ ዓመፆች ይሁኑ ጦርነቶች አንድ አምባገነን ስርዓት በሌላ አምባገነን ስርዓት እንዲተካ ምክንያት ሆኑ እንጂ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ሲገነቡ አላየንም። የዴሞክራሲ መንገድ በቃ ዴሞክራሲ ራሱ ነው።

ኢህአዴጎች ራሳቸው በዓመፅ (በጦርነት) ስልጣን ይዘው ሲያበቁ ስለ ዓመፅ መጥፎነት ይነግሩናል። ዓመፅ መጥፎ መሆኑ ቢያውቁ ለምን በደርግ ግዜ ዓመፅ ቀስቀስው ደርግን በሃይል አባረው ስልጣን ያዙ? ለምንስ አሁን በዓመፅ ስልጣን መያዝ መጥፎ ነው ይሉናል?

አዎ! ‘ደርግ ሰለማዊ የስልጣን ሽግግር ስላልፈቀደ ነው፣ ጨቋኝ ስለነበረ ነው፣ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ስላለነበረ አማራጭ አጥተን ጫካ ገብተን ከስልጣን አባረነዋል’ ይሉን ይሆናል። ልክ ነው ዓመፅ የሚነሳው በዓመፀኛ ስርዓት ነው። ስርዓት ጨቋኝ ሲሆን በህዝብ ላይ የሚፈፅመውን ግፍ ዓመፅ ይወልዳል። ስለዚህ የዓመፅን መንስኤ ህዝብ ወይ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሳይሆኑ ጨቋኝ ስርዓት ነው።

አሁን ዓመፅን እየቀሰቀሰ ያለው ማነው? ህዝብ? ተቃዋሚዎች ወይስ ገዥው ፓርቲ? ህፃናት እያደራጀ፣ ሰለማዊ ህዝብን እንዲበጠብጡ ከፍሎ እየላከ ያለው ማነው? የህዝቦችን የመሰብሰብ መብት እየነፈገ ያለው ማነው? ሰለማዊ ተቃዋሚዎችን በድንጋይ እየወገረ በሰለማዊ ትግል ተስፋ ቆርጠው የዓመፅ መንገድ እንዲከተሉ እያስገደደ ያለው ማነው? ዓመፅን የሚፈጥረው ገዥው መደብ ነው።

በኢትዮጵያ ህዝባዊ ዓመፅ ከተነሳ መንስኤው የኢህአዴግ ጭቆና ነው። በኢትዮጵያ ህዝባዊ ዓመፅ እንዳይኖር ለማድረግ ሰለማዊ የስልጣን ሽግግር በማድረግ ጭቆናን እናስወግዳለን። ከጎጂነቱ አንፃር ህዝባዊ ዓመፅን መከላከል የምንችለው ስለ ህዝባዊ ዓመፅ መጥፎነት በቲቪ በማቅረብ ሳይሆን ስልጣን የህዝብ በማድረግ ነው። ህዝብ የሚያምፀው የህዝብን ልአላዊነት ለማስከበር ነው። የህዝብን የበላይነት ለማረጋገጥ ነው። ስለዚህ ህዝባዊ ዓመፅን የምናስቀረው ስልጣን የህዝብ በማድረግ እንጂ ህዝቦችን በመጨቆን አይደለም። የህዝብን ነፃነት በማፈን ህዝባዊ ዓመፅን መከላከል አይቻልም።

አዎ! ዓላማችን ህዝባዊ ዓመፅን ማስቀረት ነው፤ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን በመገንባት።


ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ

$
0
0

Blue Advert April 12
አዲስ አበባ፡- ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹የተነጠቁ መብቶችን እናስመልስ!›› በሚል መሪ ቃል ሚያዚያ 19/2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ከአሁን ቀደም የተለያዩ ጥያቄዎችን በማንሳት ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቅም ጥያቄዎቹ ምላሽ ያልተሰጣቸው ከመሆኑም ባሻገር ጭራሹን እየተባባሱ በመምጣታቸውና ህዝብም እየተማረረ በመሆኑ ሰላማዊ ሰልፉን መጥራት እንዳስፈለገ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25 2005 ዓ.ም ያደረገውን ጨምሮ በአዲስ አበባና ሌሎች አካባቢዎች ሰላማዊ ሰልፎችንና ህዝባዊ ስብሰባዎችን ባደረገበት ወቅት የኑሮ ውድነት፣ የእምነት ጣልቃ ገብነት፣ ሉዓላዊነት፣ ዜጎችን ከቀያቸው ማፈናቀልና ሌሎችም መሰረታዊ ጥያቄዎችን አንስቶ የነበረ ቢሆንም ጥያቄዎቹ ምላሽ ሊያገኙ እንዳልቻሉ የህዝብ ግንኙነቱ ገልጸዋል፡፡ ከዚህ በተቃራኒ በእስልምና እና ኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ የሚደረገው ጣልቃ ገብነት፣ ዜጎችን ከቀያቸው ማፈናቀሉ፣ የኑሮ ውድነት፣ ሙስና አሁንም ድረስ ተባብሰው መቀጠላቸው ሰላማዊ ሰልፉን በመጥራት ህዝቡ እነዚህን የተነጠቁ መብቶች እንዲያስመለስ ማስተባበርና ማታገል የግድ በማለቱ ነው ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ ለገዥው ፓርቲ ስልጣን እንጅ ለህዝብ አገልግሎት የማይጨነቁት ተቋማት ስራቸውን በሚገባ ባለመስራትቸው ህዝብ ለከፈለው ክፍያ የሚገባውን አገልግሎት እያገኘ አለመሆኑም ሌላኛው ሰላማዊ የሰልፉ ምክንያት መሆኑን ተገልጹዋል፡፡ በተለይ የውሃ፣ የመብራት፣ የቴሌኮሚኒኬሽንና የትራንስፖርት አገልግሎቶች ህዝብን እያማረሩ መቀጠላቸው መፍትሄ ስለሚያስፈልገው የሰላማዊ ሰልፉን አስፈላጊነት እንዲሚያጎላው ኃላፊው አስታውቀዋል፡፡

ምንም እንኳ ‹‹የህዝብ መብት መነጠቅና የአግልግሎቶች እጦት ሰላማዊ ሰልፉን ወቅታዊ ቢያደርገውም የሰማያዊ ፓርቲ በአመት ውስጥ ከያዛቸው ፕሮግራሞች መካከል አንዱ ህዝብ የተቀማቸውን መብቶች ማስመለስ መሆኑንና ይህም በተደጋጋሚ በተለያዩ ሚዲያዎች መገለጹን›› አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ ገልጸዋል፡፡

ሰላማዊ ሰልፉ እሁድ ሚያዚያ 19 ከቀኑ 4 ሰዓት እስከ 8 ሰዓት ካሳንቺስ ከሚገኘው የፓርቲው ጽህፈት ቤት እስከ ጃን ሜዳ እንዲሆን የተወሰነ ሲሆን ጃን ሜዳ የተመረጠበት ምክንያትም መብቱን የተነጠቀውና ማህበራዊ አገልግሎቶችን በሚገባ ማግኘት ያልቻለው ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ጥያቄዎቹን እንዲያነሳ ሰፊ ቦታ በማስፈለጉ ነው ብለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በየ ክፍለ ከተማው የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሰላማዊ ሰልፉን ለማድረግ ዝግጅት እያደረገ እንደሆነ የገለጹት ኃላፊው ‹‹በሀይል የተቀሙትን መብቶችን ለማስመለስ በሚደረገው ጥረት ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ሲቪክ ማህበራት፣ ሚዲያውና እያንዳንዱ ዜጋ ተሳትፎ በማድረግ አገራዊ ግዴታውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
Source: – ነገረ ኢትዮጵያ

የቀደመ ውን ፍቅርህን ትተሃልና የምነቅፍብህ ነገር አለኝ።

$
0
0

ይድረስ በሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድሐኒአለም ቤተ ክርስቲያን ለምትገኙ ክርስቲያን ወንድሞቼ እና እህቶቼ፤

እንኳን ለሆሳእና በዓል በሰላም አደረሳችሁ። 

debereselam-medhanialemነበር ለካ እንዲህ ቅርብ ነበር እንዲሉ፤ ባለፉት ዓመታት ደብረ ሰላም መድሐኒአለም በሰሜን አሜሪካ ካሉ አድባራት በታላቅነቱ ከሚጠቀሱት ውስጥ ነበር ብል ማጋነን አይሆንብኝም። እኛን ምእመናኑን ሆነ እንግዶችን እጅጉን ባስደነቀ ግሩም አገልግሎት ኢትዮጵያ  ያለን እስኪመስለን ድረስ በታላቅ ደስታ አምላካችንን በቅዳሴው፣ በማህሌቱ፣ በመዝሙር ስናመሰግን ኖረናል። በእንግድነታችን ሀገር እግዚሃብሄር ፈቃዱ ሆኖ በቤተ መቅደሱ በስርዓተ ተክሊል ጋብቻ ፈጽመን፤ ልጆቻችንን በ40 ቀን በ80 ቀን አስጠምቀን፣ በስጋ ለተለዩን ጸሎተ ፍትሃት አድርሰን ለዓመታት በሰላም በፍቅር እዚህ ደርሰናል። አንዳችን ለሌላው የክፉ ቀን ደራሽ ሆነን፣ ሀዘናችንን ተጋርተን .….ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ…

 

በሰው ለሰው ድራማ ላይ ዶ/ር ሆኖ የሚተውነው አርቲስት ድራማው በግል ሕይወቱ ላይ ጉዳት እንዳስከተለበት ገለጸ

$
0
0

afro times (1)_Page_08(አፍሮ ታይምስ) ዘወትር ረቡዕ ምሽት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሚተላለፈው የ “ሰው ለሰው” ድራማ ላይ የዶክተሩን ገፀ-ባህሪ የሚጫወተው አርቲስት ልዑል ግርማ ከድራማው ጋር በተያያዘ ችግር እንደገጠመው ገለፀ።
አርቲስቱ ሰሞኑን ለአፍሮ ታይምስ እንደተናገረው በድራማው ውስጥ ዋናው ገፀ-ባህሪ (መስፍን) በደረሰበት ከባድ የመኪና ግጭት አደጋ አካሉ የማይንቀሳቀስ ከመሆኑም በላይ በውጭ አገር ታክሞ የመዳን ተስፋው የተመናመነ መሆኑ በድራማው እየታየ ሲሆን፣ ዶክተሩ “ተስፋ የለውም” ብሎ መናገሩ የችግሩ መነሻ ነው።

“ሜክሲኮ የሚገኘው ኬኬ ህንፃ ላይ ለግል ጉዳይ በተገኘሁበት ወቅት ሁለት ወጣቶች ከላይኛው ደረጃ ላይ ሆነው ‘ሌባ ዶክተር’ በማለት ጉዳት አድርሰውብኛል፤ የምኖርበት አካባቢ ሰዎችም ‘አንተ ከመቼ ወዲህ ነው ዶክተር የሆንከው?’ በሚል ‘አጭበርባሪ’ እና ‘ሌባ’ እያሉ ሰድበውኛል፤ ዘመዶቼም ለእናቴ ‘ክፉ ልጅ ከመውለድ ቢቀር ይሻል ነበር’ እያሉ መውጫ መግቢያ አሳጥተውናል” ያለው አርቲስት ልዑል ግርማ፣ “ሰዎች ገፀ-ባህሪን እና እውነተኛ ማንነትን ነጣጥለው ባለማየታቸው ለችግር ተዳርጌያለሁ” ሲል ተናግሯል።

“የድራማው ፅሁፍ ሲሰጠኝ ቀድሞውኑ እንዲህ አይነት ነገር ሊከሰት እንደሚችል ገምቼ ደራሲዎቹን አነጋግሬ ነበር” ያለው አርቲስት ልዑል፣ ይሁንና ከህክምና አማካሪያቸው ጋር ተነጋግረው የፃፉት በመሆኑ ምንም “የሚመጣ ነገር አይኖርም” በሚል አሳምነውት ስራውን እንደቀጠለ ይገልፃል። በድራማው
ላይ ለአቶ መስፍን የመዳን ተስፋ እንደሌለው መንገሩ ከአቶ አስናቀ ጋር ተሻርኮ ያደረገው የመሰላቸው የድራማው ተከታታዮች ብዙ መሆናቸውንና በዚህም በእውነተኛ ኑሮው ላይ ተፅዕኖ መፈጠሩንና ለችግር መጋለጡን የሚገለፀው አርቲስቱ “መጠየቅ ካለባቸው እንኳን ተጠያቂዎቹ ደራሲዎቹ እንጂ እኔ ልሆን
አይገባም፤ የሰራሁትም እምቢ ማለት ህዝብን መናቅ ይሆንብኛል በሚል ነው።

ደግሞም ገፀ-ባህሪው እና እውነተኛ ማንነቴ የማይገናኙ በመሆናቸው ሰዎች በእኔ ላይ ያሳደሩትን የጥላቻ መንፈስ ሊያነሱልኝ ይገባል” በማለት ለአፍሮ ታይምስ ቃሉን ሰጥቷል።

ሕወሓት ከምርጫ 2007 በኋላ ጠቅላይ ሚ/ር ለመቀየር አስቧል –ሃይለማርያም ውጣ፤ ቴዎድሮስ ግባ?

$
0
0

ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም አቶ መለስን ለመምሰል ቢሞክሩም፤ በሕወሓቶች ዘንድ ግን ማስመሰላቸው ሊዋጥላቸው አልቻለም

ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም አቶ መለስን ለመምሰል ቢሞክሩም፤ በሕወሓቶች ዘንድ ግን ማስመሰላቸው ሊዋጥላቸው አልቻለም


በሃገር ቤት የሚታተመው አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ እንደዘገበው ገዢው ፓርቲ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) በሙስና ስም የ“ማጥራት ዘመቻ” ማካሄዱን ተከትሎ በመንግሥት ሥልጣን ላይ በሚገኙ የፓርቲው አመራሮች መሐል ተከስቷል በተባለ አለመተማመንና መጠራጠር መስፈኑ ካድሬዎችን በእጀጉ እንዳስጨነቀ ተጠቆመ። ኢህአዴግን ለመሰናበት የሚፈልጉ በርካታ ካድሬዎች “ለምን” በሚል የሚቀርብላቸውን ጥያቄ ለመመለስ በመቸገራቸው ብቻ በፓርቲውን ውስጥ ለመቆየት መወሰናቸውንም ውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል።

ካድሬዎቹ ቀደም ሲል ኢህአዴግን ተሰናብተው ለወጡና በተለያዩ ግብረ ሠናይ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው በማገልገል ላይ ለሚገኙ የቀድሞ የትግል ጓዶቻቸው “በደህና ጊዜ ተገላገልክ” በሚል በፓርቲው ውስጥ ችግር ስለመኖሩ እየነገሯቸው መሆኑን የጠቀሰት የዜና ምንጮቹ፣ ለስራ ከሃገር መውጣት የማይችሉ ባለስልጣናት ጭንቀት ውስጥ መግባታቸውን ይናገራሉ። ለሃላፊዎቹ ደህንነት ሲባል የሚሰሩበትን ተቋምና ስም መናገር እንደማይችሉ በመጥቀስ መረጃውን የሰጡት ክፍሎች “ባለስልጣኖቹ በመካከላቸው እርስ በርስ መተማመን በመጥፋቱ ችግራቸውን መወያየት እንኳን አይችሉም” ብለዋል፡፡

“በጣም የሚቀርቡኝ ጓደኞቼ ገንዘብ ወደ ውጪ እንድወስድላቸው እስከመጠየቅ ደርሰዋል” ሲሉ የገለጹት አነድ የቀድሞ የኢህአዴግ ባለስልጣን፣ ፓርቲው በሙስና ስም ያካሄደው የሽግግር ወቅት የማጥራት ርምጃ የፈጠረው ስሜት አሁን ድረስ እንዳለ ጠቁመዋል። ሰሞኑንን ወደ አሜሪካ ያቀኑ
የቀድሞ የኢህአዴግ አመራር “ኢህአዴግ በከፍተኛ የመበስበስ አደጋ ውስጥ ይገኛል። በዚህም የተነሳ ካድሬው ተዥጎርጉሯል” ሲሉ መናገራቸውም ተገልጿል።

Ethiopian regime’s foreign affairs minister Teodros Adhanom warns ENTC over Nile damይሕ በእንዲሕ እንዳለ የየኢሕአዴግ አባል ድርጅት የሆነው ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሐት) ከምርጫ 2007 በኋላ ለሁለት ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የተሾሙትን ኃይለማርያም ደሳለኝን በውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቴዎድሮስ አድሃኖም ለመተካት እንቅስቃሴ መጀመራቸው በፓርቲው ውስጥ
ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ሪፖርት መቅረቡ ተሰምቷል። ይኽው ሪፖርት የቀረበላቸው ክፍሎች ቀደም ሲል እንዳደረጉት የህወሐትን ከፍተኛ አመራሮች በማነጋገር እየወተወቱ (ሎቢ እያደረጉ) መሆናቸውን ውስጥ አዋቂ ምንጮቹ ተናግረዋል።

ምንጭ አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ (በሃገር ቤት የሚታተም)

Sport: [የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጉዳይ] ዘመናዊነት ከፍተኛ ደመወዝ የሚከፈለው አሰልጣኝ መቅጠር ብቻ አይደለም

$
0
0

(በመንሱር አብዱልቀኒ – በኢትዮስፖርት ጋዜጣ ላይ ታትሞ የወጣ)

walia
ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ ጠዋት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ መሾሙን የሚገልጹ መረጃዎች ከወጡ በኋላ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፈጥኖ ማስተባበያ ልኳል፡፡ ረፋዱ ላይ የሹመቱ ዜና እንደተነገረ ከቀትር በኋላ የፌዴሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት ተከታታይ የማስተባበያ ፕሬስ ሪሊዞች በትኗል፡፡ ፌዴሬሽኑ የቀድሞውን የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ስፖርት አምድ አዘጋጅ አቶ ወንድምኩን አላዩን በህዝብ ግንኙት ኃላፊነት መሾሙ ይታወቃል፡፡ በአቶ ወንድምኩን የግል ኢሜይል አድራሻ በኩል የፌዴሬሽኑ ኦፊሴላዊ መግላጫዎች፣ ዜናዎችና ጥቆማዎች ለመገናኛ ብዙሃኑ በኢሜይል ይላካሉ፡፡ ከአቶ ወንድምኩን ሹመት በፊትም በሚድያው አባላት ዘንድ ክብርና ተወዳጅነትን ያተረፈችው ወይዘሮ ዘውድነሽ ይርዳው የተቋሙን የህዝብ ግንኙነት ክፍተቶች በብቃትና በታታሪነት ስትሸፍን ትልቁ የመገናኛ መሳሪያዋ ኢሜይል ነበር፡፡ አስቸኳይ ጋዜጣዊ መግለጫ ቢዘጋጅ ወይም ተቋሙ የሚልከው ሰበር ዜና ቢኖር አንድ ጋዜጠኛ በሞባይል ስልኩ በኩል ባለበት ቦታ መልዕክቱ ይደርሰዋል፡፡

ማክሰኞ ከሰዓት በኋላ የግል ስልኬ ደጋግሞ ምልክት ይሰጠኝ ነበር፡፡ ከፊሉ በዕለቱ ለንባብ የበቃችው ኢትዮ-ስፖርት በርዕሰ አንቀጿ ስለሰጠችው ጥቆማ የሚናገሩ መልዕክቶች ሲሆኑ አራቱ ደግሞ ከአቶ ወንድምኩን አላዩ የተላኩ የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ፕሬስ ሪሊዞች ነበሩ፡፡ የህዝብ ግንኙነቱ ክፍል በዕለቱ በህዝቡ ዘንድ የተፈጠረውን የመረጃ ግርታ ለማጥራት በተከታታይ ማብራሪያዎችንና ማስተካከያዎችን ያከሉ መግለጫዎችን ልኳል፡፡ ፈጥኖ መረጃን ማስተካከል እጅግ ዘመናዊነት በመሆኑ አቶ ወንድምኩንና ዴፓርትመንታቸው ሊመሰገኑ ይገባል፡፡

ፌዴሬሽኑ ደጋግሞ እንዲያስተባብልና ብዥታውን እንዲያጠራ የተገደደበት ምክንያት የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ሹመት ከፍተኛ የህዝብ ትኩረት በመሆኑ ነው፡፡ ተሹዋሚውን መምረጥ እንደቀድሞው ቀላል አይደለም፡፡ ከሚድያውም ሆነ ከህዝቡ ብዙ ጥያቄዎችን ያስከትላል፡፡ የአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ቡድን በአፍሪካ ዋንጫና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ላይ ባሳየው እመርታ የዋልያዎቹ ነገር ዓብይ የህዝብ ትኩረት ሆኗል፡፡ መገናኛ ብዙሃንም ተሹዋሚው ማን የመሆኑን ዜና ለህዝብ የማሳወቅ የጓጉትም ለዚህ ነው፡፡

በሚድያውና በህዝቡ ትኩረት ምክንያት ፌዴሬሽኑ የአሰልጣኙን ሹመት ይፋ ለማድረግ ጫና ውስጥ ሳይገባ አልቀረም፡፡ በእርግጥ ብሔራዊ ቡድን ያለአሰልጣኝ መቆየት አይገባውምና ፈጥኖ ቢሾም መልካም ነበር፡፡ ይህኛው ጫና ግን ከዚህ አንጻር ሳይሆን የህዝቡና የሚድያው ጉጉት ከማየሉ ጋር ተያይዞ የመጣ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡

የህዝብ፣ የመንግሥት እና የፌዴሬሽኑ ትኩረት ከፍ ያለ ደረጃ ላይ የሚገኝ አሰልጣኝ መቅጠር ላይ ብቻ ካተኮረ ግን ስህተት ነው፡፡ በፌዴሬሽኑ አካባቢ ያሉ ታማኝ ምንጮች ለኢትዮ-ስፖርት እንደገለጹት መንግሥትም ሆነ ፌዴሬሽኑ ብሔራዊ ቡድኑን ከቀደሙት ስኬቶች በላይ ሊያደርስ ይችል ዘንድ የታመነበት አሰልጣኝ መሾሙ ላይ አተኩረዋል፡፡ በዚህ ረገድ የመንግሥትም እርዳታ መኖሩ እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡ ዘመናዊ ጎዳናን ለመከተል ዘመናዊ አስተሳሰብ ያለው አሰልጣኝ ጠቃሚነቱ አያጠራጥርም፡፡ ሆኖም ዘመናዊነት ከፍተኛ ደመወዝ የሚከፈለው አሰልጣኝ መቅጠር ብቻ አይደለም፡፡ በብሔራዊ ቡድኑ ቴክኒካዊ አስተዳደር ላይ በግልጽ የሚታይ ለውጥ ካልኖረ አንድን ባለሙያ ብቻ መሾም ፍሬ አይኖረውም፡፡

ለምሳሌ፡- በወር 20ሺህ ዶላር የሚከፈለው አሰልጣኝ ሊቀጠር ይችላል፡፡ የቅጥሩን መመዘኛ አሟልቷል የተብሎ የሚሾመውን ባለሙያ ደመወዝ መክፈል ብቻ የዕድገቱ መንገድ አይሆንም፡፡ አሰልጣኙ በዘመናዊው የእግር ኳስ ዓለም ውጤታማ አሰልጣኞች ሊያገኙ የሚገባውን ድጋፍ ከፌዴሬሽኑና በዙሪያው ካሉ የብሔራዊ ቡድኑ የስልጠና ባልደረቦቹ የሚያገኝበት ሜዳ የተጠረገ ሊሆን ይገባል፡፡ በዚህ ረገድ እግር ኳስ ፌደሬሽኑ የአመለካከትና መሰረታዊ የአሰልጣኞች ስታፍ መዋቅራዊ ተሃድሶ እንደሚያስፈልገው ደፍሬ እናገራለሁ፡፡
walia
ቀጣዩን የብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ለመቅጠር ኃላፊነት የተሰጣቸው አካላት የቡድኑ የቴክኒክ አስተዳደር የሚሻሻልበት ኦፊሴላዊ ፕሮፖዛል ለስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ወይም ለሚመለከተው አካል ቢያቀርቡ መልካም ነው፡፡ አዲሱ ተሹዋሚ ከዘመኑ እግር ኳስ ጋር የሚራመድ እስከሆነ ድረስ ለውጤታማነቱ ዘመናዊ አሰራርን ገቢራዊ ለማድረግ የተዘጋጀ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ያረጀውንና በብሔራዊ ቡድኖቻቸው የተለመደውን አሰራር አሽቀንጥሮ ለመጣል ማመንታት የለብንም፡፡ አዲስ አቀራረብ ብሔራዊ ቡድኑን ለበለጠ ውጤት ለማድረስ እንደሚበጅ አምነን ከዘመኑ ጋር ለመራመድ መዘጋጀት አለብን፡፡

ረዳቶች

የ20 እና የ30ሺህ ዶላር አሰልጣኝ ብልህ ረዳቶችና ከረዳቶቹም ጋር ለውጤታማነት የሚሰራበት ሲስተም ይፈልጋል፡፡ ምክትል አሰልጣኝ ለመሾሙ ነገር በዋና አሰልጣኙ መልካም ፈቃድ እንጂ በፌዴሬሽኑ ብቸኛ ጥቆማ ከተወሰነ የስህተቱ መጀመሪያ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ተሹዋሚው ረዳቱን የመምረጡ አብላጫ የመወሰን ድምጽ ሊነጠቅ አይገባም፡፡ ምን ያህል ረዳቶች እንደሚያስፈልጉት መወሰንም የተሹዋሚው ውሳኔ መሆን አለበት፡፡ አዲሱ አሰልጣኝ በውሳኔዎችና በዕቅዶች ላይ ተጨባጭ መነሻና ምክንያት ያላቸውን ብሩህ ረዳቶች (ከተሟላ የስራ መመሪያ ጋር) ይፈልጋል፡፡ የብሔራዊ ቡድኑ የተጫዋቾች ምርጫ በቀደመ ዝና እና ባለፈ ረከርድ የመሆኑ አሮጌነት አብሮን ሊጓዝ አይገባም፡፡ ለአከራካሪ ምርጫዎች ጥልቅ ትንተና ያስፈልገናል፡፡ የቪዲዮ ማስረጃዎችና ትንተናዎች በዘመኑ እግር ኳስ ደጋፊ ናቸው፡፡ ከሹመቱ ጋር ተቋሙ የአሰልጣኞች ስታፉ ከጠለቀ እይታና ትንተና በመነሳት የቡድን ግንባታ ሂደቱን የሚፈጽም እንዲሆን አመቺ ከባቢ መፍጠር አለበት፡፡ ብሔራዊ ቡድን ብሔራዊ ምልክት እንደመሆኑ በኮስታራ አስተዳደር ስር መግባት ይኖርበታል፡፡ ኢትዮጵያዊያን ተጫዋቾችን ለቡድኑ ምርጫ ለማብቃት ብቃታቸውን ለመገምገምና ካስፈለገም ለትውልድ ሃገራቸው እንዲጫወቱ ለማግባባት አሰልጣኞች ወደየትም ሃገር መጓዝ እንዲችሉ በፋይናንስ ምክንያት መገደብ የለባቸውም፡፡ ዋና አሰልጣኙ በአዲስ አበባ በሚደረጉ የሊግ ጨዋታዎች ላይ ቢያተኩር እንኳን በክልል የሚደረጉ ግጥሚያዎችን ለመገምገም ረዳቶቹን ለመላክ የፋይናንስና የቢሮክራሲ አፈጻጸም ዝግጁነት ያስፈልገዋል፡፡ እገሌ የተባለውን ረዳት ወደ ሐረር ወይም አርባ ምንጭ ለመላክ ዋና አሰልጣኙ መቸገር የለበትም፡፡ ነገ ዛሬ ሳይባል ለተልዕኮው የትራንስፖርትና የሆቴል ወጪው ሊሸፈንለት ያስፈልጋል፡፡ ረዳቱም ከዋና አሰልጣኙ በሚሰጠው መስፈርት መነሻነት ገምግሞ እንደነገሩ ገጽ የሞላ ፍሬ የለሽ ጽሁፍ ማቅረብ የለበትም፡፡ በቴክኒክና ታክቲካዊ ነጥቦች የጠለቀ፣ አሳማኝ ጥቆማና የተብራሩ ትንተናዎችን በማቅረብ በቦታው ላልተገኘው ዋና አሰልጣኝ ያልተዛነፈ ማስረጃ ካላቀረበ ትርፉ ድካምና ወጭ ብቻ ይሆናል፡፡

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጋጣሚዎች ለጥልቅ ትንተና በሚያመች መልኩ ጨዋታዎቻቸውን ገምግመው አያውቁም፡፡ ሶስት አራት ጊዜ የጨዋታዎችን ቪዲዮ መመልከትና እርግጠኛነት የጎደላቸው በወፍ በረር የተለኩ መረጃዎችን ማቅረብ ጊዜ አልፎባቸዋል፡፡ የሱዳኑ ሂላል ክለብ ሁለት የቪዲዮ ተንታኞች እንዳሉት አውቃለሁ፡፡ ሁለቱ ባለሙያዎች የአሰልጣኝነት ማዕረግ ያላቸው አለመሆናቸው ለሃገራችን እግር ኳስ አስገራሚ ሊሆን ይችላል፡፡ ከፍ ካለም የጨዋታዎች ትንተና የደረሰበትን ርቀት መመልከት እንችላለን፡፡ ሪያል ማድሪድ ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር ባደረገው የስፔን ጥሎ ማለፍ ዋንጫ የደርሶ መልስ ጨዋታ በአሰልጣኙ (በብቁ ረዳቶች ድጋፍ ማግኘታቸውን አትዘንጉ) የቀረበው የቴክኒካዊ ግምገማ ሪፖርት ባለ 73 (ሰባ ሶስት) ገጽ ነበር፡፡ ፔፕ ጋርዲዮላ በባርሴሎና ኃላፊነቱ ወቅት ለአንድ ጨዋታ 93 (ዘጠና ሶስት) ገጽ ሪፖርት ማቅረቡን አውቃለሁ፡፡ ቁጥሮቹን በአሃዝና በፊደል የጻፍኩት ምናልባት አንባቢ የትየባ ስህተት ተፈጽሞ እንደሆነ እንዳይጠራጠር በማሰብ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ በድን በሪያል ማድሪድና ባርሴሎና ደረጃ መታየት አለበት እያልኩ አይደለም፡፡ ደረጃችን የሰማይና የምድር ያህል መለያየቱን አልክድም፡፡ የዘመኑ እግር ኳስ የቡድን ዝግጅት የት እንደደረሰ ለመጠቆም ፈልጌ ነው፡፡ የዋልያዎቹ ነገር እንደ አቅሙ ከዘመኑ ጋር መራመድ ካለበት ግን የራሱን ተጨማሪ የዕድገት ርቀት መጓዝ ግዴታው ይሆናል፡፡

የአካል ብቃት ዝግጁነት፣ ተደጋጋሚው ጩኽት

ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ የአካል ብቃት እና የጉዳት መከላከል ዝግጁነት ነው፡፡ ተደጋግሞ እንደተነገረው ካለፈው ተሞክሯችን መነሻነት ብሔራዊ ቡድኑ የአካል ብቃት አሰልጣኝ ይፈልጋል፡፡ የ20ሺህ ዶላሩን አሰልጣኝ ሁሉን ለብቻው እንዲሰራ በኮንትራት ውሉ ላይ ልናስገድደው አንችልም፡፡ ብቻውን ሊሰራ ውል የሚፈጽም አሰልጣኝ ቢኖር እንኳን በሌላ ቦታ በቂ የስራ ዕድል የሌለው ብቻ ነው፡፡ ኮስታራ ባለሙያ በሁሉ ረገድ ፕሮፎሽናል አቀራረብን ይከተላል፡፡ 10 ድስት ጥዶ አንዱም የማይበስልለት አይደለም፡፡ እንደ አሰልጣኞች ስታፍ አለቅነቱ በነገሮች የመወሰን መብት ያለው መሆኑን የሚያውቅ መሪ በተግባር ክፍፍል ያምናል፡፡ እግር ኳስ በሜዳ ላይ ብቻ ሳይሆን በአሰልጣኞች ስታፍ ውስጥም የቡድን ስራ ነው፡፡ ዘርፉ የአካል ብቃት ላይ ብቻ እውቀትና አንጻራዊ ስኬታማ ተሞክሮ ያለውን ባለሙያ ይፈልጋል፡፡ ክለቦቻችን በዚህ የዘመናዊነት እርከን ላይ የመራመድ ባህል ስለሌላቸው ብሔራዊ ቡድኑም በተመሳሳይ አሰራር ስር ሲንገታገት ኖሯል፡፡ የምንገጥመውን ቡድን ጠንካራና ደካማ ጎን ለማወቅ መትጋት ያለብንን ያህል ተጫዋቾች ተሰጥኦዋቸውን በሜዳ ላይ ተግባራዊ ለማድረግ የሚረዳቸውን ሙሉ የአካል ብቃት ሁልጊዜ ማግኘት አለባቸው፡፡ ይህ ደግሞ በመስኩ ባለሙያ ብቻ የሚሰራ ነው፡፡ ፌዴሬሽኑ አመራሮች ለዚህ ሃሳብ ጀርባቸውን መስጠት የለባቸውም፡፡ ፉትቦል አካላዊም ስፖርት መሆኑን መዘንጋት መሳሳት ነው፡፡

የፕሬስ አታሼ ነገር

ብሔራዊ ቡድኑ የራሱ የሆነ የፕሬስ አታሼ ይፈልጋል፡፡ ለቡድኑ ውጤታማነትን የሚመኝ አመራር በቡድኑና በህዝቡ መካከል ያሉትን መገናኛ ብዙሃን በዘመናዊ ስርዓት ማገናኘት አለበት፡፡ ብሔራዊ ቡድኑ ዝግጅትና ጨዋታ በሚኖሩት ጊዜ በዙሪያው የሚወጡትን መረጃዎች ለሚድያው የሚያቀብል፣ ጋዜጣዊ መግለጫዎችን የሚያዘጋጅ፣ መዘጋጀታቸውን ለሚያድያው የሚያሳውቅ፣ የሚድያውን አባላት የሚያስተናግድ፣ ለአንድ ለአንድ ቃለምልልሶች የሚያስተባብርና ከላይ በተጠቀሱት ወቅቶች ቡድኑን በተመለከተ በራሱ ቃለምልልሶችን የሚሰጥ የፕሬስ አታሼ ያስፈልገዋል፡፡ የፕሬስ አታሼ እና የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አንድ አይደሉም፡፡ የፕሬስ አታሼው የብሔራዊ ቡድኑ ጉዳይ ብቻ የሚመለከተውና ሹመቱም ከቡድኑ ጋር የተሳሰረ ባለሙያ ነው፡፡ ቡድኑ በሄደበት ሃገር ሁሉ አብሮ ይጓዛል፡፡ የቡድኑ አንድ አባል የሚያገኘውን ጥቅምና መስተንግዶ ሁሉ በማግኘት ይሰራል፡፡ እግር ኳስ ተጫዋቾች ከልምምድ በኋላ ለማዕድ ይሰበሰባሉ፡፡ ከዚያም ዕረፍት ይወስዳሉ፡፡ ከዚህ ቀደም እንደታየው በማረፊያ ሰዓታቸው ሚድያውን ለማስተናገድ ሊገደዱ አይገባም፡፡ በጋዜጠኞች የስልክ ጥሪ መረበሽ የለባቸውም፡፡ ይህ ለአሰልጣኞቹም ይሰራል፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በዚህ ረገድ የደረሰባቸውን አለመመቸት ያውቁታል፡፡ ተጫዋቾችም እንዲሁ፡፡ ያለፈውን ስህተት በመማሪያነት በመጠቀም እርምት ያስፈልገናል፡፡
serebian ethiopia coach
ተጫዋቾች ከመገናኛ ብዙሃን ጋር ያላቸው የስራ ግንኙነት ቢያንስ የህዝብ በሆነው ብሔራዊ ቡድን ስርዓት መያዝ አለበት፡፡ በቡድኑ ዙሪያ በየዕለቱ የሚፈጠሩ አዳዲስ ጉዳዮችም ስርዓትን በጠበቀና የቡድኑን የዝግጅት ትኩረትና ዕረፍት ባላሳነሰ መልኩ ለሚድያው መድረስ ይኖርባቸዋል፡፡ ከ20 ዓመታት በፊት ከሁለት ሬዲዮ ጣቢያዎችና አንድ ቴሌቪዥን በስተቀር አልነበረንም፡፡ ዛሬ በአዲስ አበባ ብቻ ሶስት ቴሌቪዥን እና ስድስት ሬዲዮ ጣቢያዎች አሉን፡፡ በየክልሉም ተበራክተዋል፡፡ ለእግር ኳሱ ሽፋን የሚሰጡ በርካታ ጋዜጦችና መጽሔቶችም አሉ፡፡ የሙዚቃና የመዝናኛ ሬዲዮ ፕሮግራሞች ለእግር ኳስ መደበኛ ሽፋን መስጠታቸው ተለምዷል፡፡ በዋና ጸኃፊነት እንደማገለግለው የኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር እይታ ከ100 በላይ የስፖርት ጋዜጠኞች በመላው ሃገሪቱ ይገኛሉ፡፡ የብሔራዊ ቡድኑ የፕሬስ አቀራረብ ግን ከ20 ዓመት በፊት በነበረበት አቋም ላይ እንዳለ ነው፡፡ ይኽው አመለካከት ተሃድሶ ይፈልጋል፡፡ ከዘመኑ ጋር መራመድ ይኖርበታል፡፡ በእግር ኳሱ ዓለም ውጤታማነት የተለያዩ ሚናዎች ውህደት እንጂ የአንድ አሰልጣኝ ብቃት ብቻ አይደለም፡፡ ዋና አሰልጣኙ የነገሮች ሁሉ የበላይ አለቃ እንጂ የነገሮች ሁሉ ፈጻሚ ሊሆን አይችልም፡:

ምንጭ – ኢትዮ-ስፖርት ጋዜጣ (ከሃገር ቤት)

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live