Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

Health: ትኩሳትና ህመሞቻችን የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች

$
0
0

ሁላችንም ከዚህ በፊት ትኩሳት አጋጥሞን ያውቃል- ቢያንስ በጉንፋን እንኳ ታሞ የማያውቅ የሚኖር አይመስለንምና፡፡ ከመነሻው ስንጀምር ትኩሳት በራሱ በሽታ አይደለም፡፡ ነገር ግን የእልፍ አዕላፍ በሽታዎች /በተለይም የኢንፌክሽኖች/ ቋሚና ጠቋሚ ምልክት ነው፡፡ ለመሆኑ ይህ ሁላችንም በቅርበት የምናውቀው የበሽታዎቻችን ታርጋ በራሱ ምንድን ነው? በአስገራሚ ሁኔታ እስካሁን የስነ ህይወት ሳይንስ ለዚህ ጥያቄ መቶ በመቶ የሚያስመካ መልስ ለማግኘት አልቻለም፡፡

hot pain በጥቅሉ ተመራማሪዎችን የሚያስማማ አንድ ማብራሪያ አለ፡፡ የሰውነታችን የሙቀት መጠን በጤናማው ክልል ውስጥ እንዲቆይ የሚያደርገው ‹‹›ሃይፓታላመስ›› የተባለው የአንጎል ክፍል ነው፡፡ ሰውነታችን ውስጥ ኢንፌክሽን ሲፈጥር ለመዋጋት የሚታትሩ ነጭ የደም ህዋሳት የተለያዩ ኬሚካሎችን በደማችን ውስጥ ይለቃሉ፡፡ ከእነዚህ ኬሚካሎች ውስጥ ሁለቱ /IL-1,TNF-1/ ወደ አንጎል በመዝለቅ የአንጎልን አሳር የሚያቀውሱ ሌሎች ኬሚካሎች /prostaglandins/ እንዲፈጠሩ ያደርጋል፡፡ የተለያዩ የአንጎል ክፍሎች በእነዚህ ኬሚካሎች የተነሳ ይታወካሉ፡፡ በኢንፌክሽን ወቅት የአስተሳሰብ ብዥታና የማገናዘብ ብቃት መውረድ የሚመጡባቸው ምክንያቶች አንዱ ይህ ነው፡፡ የሰውነት ሙቀት የሚቆጣጠረው ነው ‹‹ሃይፓታለመስ››ም የተመሳሳይ ክስተት ሰለባ ይሆናል፡፡

ሃይፓታለመስ በኬሚካሎቹ ጥቃት ሲደርስበት ጤናማ ብሎ መዝግቦት የነበረው የሙቀት መጠንን ይለውጥና ከዚያ የሚበልጥ ሙቀትን በሰውነት ላይ ለማምጣት ይጥራል፡፡ ብርድ ብርድ ማለትንና መንቀጥቀጥ፣ የጥርስ መንገጫገጭ የሚመጡትም በሃይፓታላመስ የታዘዘውን ከፍ ያለ የሰውነት ሙቀት ለማምጣት ነው፡፡ የሰውነት ህዋሳት ወትሮ በላቀ መልኩ ኢነርጂ የማቃጠል ሂደት ይታይባቸዋል፡፡ በገፍ የተቃጠለው ኢነርጂ ደግሞ ከፍተኛ ሙቀትን /ትኩሳትን/ ያመጣል፡፡ ቀጥሎ የሚታየው በላብ መዘፈቅ ደግሞ ሃይፓታላመስ እየናረ የመጣውን የሰውነት ሙቀት ለማውረድ የሚያደርገው የመልሶ ማቀዝቀዝ ጥረት አካል ነው፡፡ ይህ አይነቱ ውሃ ቅዳን ውሃ መልስ ድግግሞሽ ኢንፌክሽኑ እስካለ ድረስ ይቀጥላል፡፡

ትኩሳትን ሁላችንም የምናየው በፍራቻና በቂም አይን ነው፡፡ ነገር ግን ትኩሳት ተፈጥሯዊ ሂደት መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ ተፈጥሯዊ ሂደት ደግሞ ከጀርባው የሚያስከትለው ጠቀሜታ አያጣም፡፡ ትኩሳትም በኢንፌክሽን ለተጠቃው ሰውነት የሚያበረክተው ጥቅም ይኖራል፡፡ በአንድ በኩል የናረው የሰውነት ሙቀት በኢንፌክሽን ፈጣሪ ጥቃቅን አካላት /ባክቴሪያና ፓራሳይት/ ርቢ እንዳይፋፋም ያደርጋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የነጭ ህዋሳት የአመራር ሂደት እንዳይቀላጠፍ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፡፡ ድካምና እንቅልፍ እንቅልፍ እንዲሰማው በማድረግ ህሙማን ኢነርጂ እንዲቆጥቡም ያስገድዳቸዋል፡፡
ይህ ጠቀሜታ ግን ትኩሳት ከሚያስከትለው መዘዝ ጋር ሲወዳደር ዶሮን በቆቅ እንደመለወጥ ይቆጠራል፡፡ ትኩሳት የሰውነትን የኢነርጂ ጥሬ ክምችት ይፈጃል፡፡ መክሳትና አቅም ማጣትንም ያስከትላል፡፡ የሰውነት የፈሳሽ ክምችትን በሟሟጠጥም ለፈሳሽ እጥረት ይዳርጋል፡፡ ትኩሳቱ ኃይለኛ ከሆነ ደግሞ ራስን መሳትንና የሚጥል ህመምን የሚመስል መንቀጥቀጥ /በተለይ በህፃናት ላይ/ ያመጣል፡፡ ዝርዝሩ ብዙ ነው፡፡

እንግዲህ ትኩሳትን በህክምና ለማለዘብ ጥረት የሚደረገውም ለዚህ ነው፡፡ መድኃኒት ከመውሰድዎ በፊት በቤትዎ ሊያደርጓቸው የሚችሉት አንዳንድ እርምጃዎችን እንመልከት፡፡
- ፈሳሽ በብዛት ይውሰዱ፡፡
- በቀዝቃዛ ውሃ በራሰ ጨርቅ ሰውነትዎን ያብሱ
- ፈሳሹ ከውሃ ይልቅ አልኮል /መጠጥን ሳይሆን የህክምናውን አልኮል/ ቢሆን ይመረጣል
- በጣም ስስና ሙቀትን የሚያሳልፍ ልብስ ይልበሱ
- አንሶላ፣ ጋቢ፣ ብርድ ልብስ… ‹‹ብርድ ይመታሃል›› ለሚለው የከተማ አፈታሪክ ከመገዛት ውጭ አይጠቅምዎትም፤ እንዲያውም ትኩሳቱን ያፋፍሙታል፡፡ ይህን ሁሉ ሲያደርጉ ግን የትኩሳቱ መንስኤ የሆነውን ዋናውን ህመምዎን መመርመርና መታከም እንዳለብዎ አይዘንጉ፡፡ ትኩሳት ምልክት እንጂ በራሱ ህመም አይደለም፤ እሱን ማስታገስ ለበሽታው መዳን ዋስትና አይሆንም፡፡

ከላይ ያየናቸውን እርምጃዎች ወስደው አሁን ትኩሳትዎ ጋብ ካላለ ያለ ሐኪም ትዕዛዝ የሚሸጡ ማስታገሻዎችን ከየትኛውም መድኃኒት ቤት መግዛት ይችላሉ፡፡ ፓራሴታሞል ፍቱን ሲሆን ነገር ግን ያልተፈለጉ የጎንዮሽ ጉዳቶች /side effect/ እምብዛም የሌሉት ግሩም መድኃኒት ነው፡፡ እንደ አስፕሪን እና ዳይክሎ ፌናክ አይነቶቹ መድኃኒቶች ከፓራሴታሞል የበለጠ ፍቱንነት ቢኖራቸውም የጨጓራ ህመምን ከማባባስ ጀምሮ ሌሎች ያልተፈለጉ ውጤቶችን ስለሚያመጡ በሐኪም ካልታዘዘልዎ በቀር ባይወስዷቸው ይመረጣል፡፡


የአንድነት ፓርቲ የመጪው ጊዜ ፈተና –ከፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)

$
0
0

የግል አስተያየት

“አዲሱ” የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ግዛቸው ሺፈራው ከሪፖርተር ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ስለመጪው የፖለቲካ እርምጃቸው እንዲህ ይላሉ ፦
” ከኢሕአዴግ ጋር ገንቢ ግንኙነት (Constructive Engagement) እንዲኖረን እፈልጋለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የጥላቻ ፖለቲካ ማብቃት አለበት፡፡ ኢሕአዴግ ተቃዋሚዎችን የሚያያቸው እንደ ጠላት ከዚያም አልፎ እንደ ሽብርተኛ ነው. . . በእኛም በኩል ኢሕአዴግን የምናየው እንደ አውሬ ነው፡፡ ምናልባት የሠራውን ሥራ ሁሉ ዋጋ (Credit) ያለመስጠት አለ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፖለቲካችን ኢሕአዴግን መቃወም ብቻ ሆኖአል፡፡ ያ መቆም አለበት፡፡ ትልቁ ኳስ ያለው ኢሕአዴግ ዘንድ ነው፡፡ እኔ በበኩሌ ወደፊት በማደርገው እንቅስቃሴ ገንቢ ግንኙነት አድርገን ያለውን የፖለቲካ ምኅዳር ለሁላችንም እኩል ማድረግ አለበት፡፡”
GizachewShiferaw
ይህ መንገድ፣ ካልተሳሳትኩ ” ሶስተኛው መንገድ” ( The Third Way) የሚባለውና አቶ ልደቱ አያሌው የ1997 ምርጫ አጣብቂኝ በገባበት ወቅት አምጥተው የደነጎሩት፣ በሌላ አነጋገር “መሀል ላይ መቆም” የሚባለው የፖለቲካ አካሄድ ነው። አሪስቶትል “መሀል ላይ መቆምን” ወርቃማ የፖለቲካ አካሄድ ነው ይለዋል ( The Golden mean- ) ። መሀል ላይ ቆመው የሚታገሉ ፖለቲከኞች ጫፍ እና ጫፍ ከቆሙት የፖለቲካ ሃይሎች ጋር ሳይጋጩ ፣ ሁለቱንም መስሎ በመኖር ወይም ከሁለቱም ጫፎች የተወሰኑትን አስተሳሰቦች በመውሰድ የራስ አድርጎ በመታገል ያምናሉ ። “የመሃል ፖለቲካ” ምን ያክል ርቀት እንደሚወስድ በዚህ ዙሪያ የተሰሩ ትምህርታዊ ጥናቶችን ባላነብም፣ ሀሳቡን ሲያራምዱ የነበሩት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ቢል ክሊንተንም ሆኑ የቀድሞው የእንግሊዝ ጠ/ሚ ቶኒ ብሊየር ብዙ ርቀት እንዳልሄዱበት የሁለቱንም መጽሃፎች አንብቤ ተረድቻለሁ ። ዛሬም ቢሆን ዲሞክራቶችና ሪፑብሊካኖች ዳር እና ዳር ቆመው የአሜሪካን ፖለቲካ ይዘውሩታል፣ በእንግሊዝም ሌበርና ኮንሰርቫቲቮች ዳር እና ዳር ቆመው ይተያያሉ።

“መሃል ላይ የቆሙ” ፖለቲከኞች የራሳቸው የሆነ የፖለቲካ ፕሮግራም የላቸውም ተብሎ ስለሚታሰብ፣ ብዙውን ጊዜ በወላዋይነት ይከሰሳሉ፣ በምርጫ ጊዜ ድል የሚቀናቸውም አልፎ አልፎ ነው። ዲሞክራሲ በሆኑ አገሮች “መሀለኞች” የመመረጥ እድል የሚያገኙት ህዝቡ ጫፍና ጫፍ በቆሙ ፖለቲከኞች መሰላቸት ሲጀምር ብቻ ነው ፤ አምባገነንነት በሰፈነባቸው አገሮች ደግሞ መሀል ላይ የሚቆሙ ፖለቲከኞች ፈሪዎች ተደርገው ስለሚቆጠሩ ብዙም አይወደዱም። መሀል ሰፋሪዎች መሀል ላይ የሚቆሙት ከመንግስት የሚወርደውን ዱላ ስለሚፈሩ ነው ተብሎ ይታማሉ። አቶ ልደቱ አያሌው በ97ቱ ምርጫ “መሀል ላይ የመቆምን” ፖለቲካ ማራመድ ሲጀምሩ ደጋፊዎቻቸው በሁለት ምክንያቶች አልተቀበሉዋቸውም ነበር ፤ አንደኛው ምክንያት ምርጫውን ያሸነፉት “ዳር” ላይ ቆመው ባራመዱት የፖለቲካ አቋም እንጅ በሁዋላ ላይ ባመጡት “የመሀል ፖለቲካ” አስተሳሰብ ስላልነበረ፣ ደጋፊዎቻቸው አዲሱን ባህሪ ለመቀበል አልቻሉም ። አቶ ልደቱ የጨዋታውን ስልት ወደ ምርጫ ከመግባታቸው ቀደም ብሎ ቢያስታውቁ ኖሮ ሁዋላ ላይ የደረሰባቸውን አይነት ውግዘት አይደርስባቸውም ነበር፣ በምርጫውም ላያሸነፉ ይችሉ ነበር።

ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ አቶ ልደቱ የጨዋታውን ህግ የቀየሩት በደህንነት ሃይሎች ብዙ እንግልትና ማስፈራሪያ ከደረሳቸው በሁዋላ በመሆኑ የአቋም ለውጡ ከፍርሃት ጋር ተያይዞባቸዋል። ጀግንነትን የሚያወድሰው የኢትዮጵያ ህዝብ ከመንገዱ ትንሽ ሸርተት ያለን ሰው በወላዋይነትና በፈሪነት ፈርጆ ይጠለዋል ።

ኢ/ር ግዛቸውም የመሀሉን ቦታ ይዘው እንደሚታገሉ አስታውቀዋል። እዚህ ላይ ሁለት ነጥቦችን እናንሳ። አንድነት ፓርቲ ከኢህአዴግ ጋር መልካም ግንኙነት ከማድረጉ በፊት በቅድሚያ በኢህአዴግ በኩል የሚቀርበውን ቅደመ ሁኔታ መቀበል አለበት፣ ያም ቅደመ ሁኔታ “የምርጫ ስነምግባር መመሪያ” ውን መፈረም ነው። መድረክና አንድነት ይህን መመሪያ አንፈርምም ብለው ላለፉት 6 ዓመታት በአቋማቸው ጸንተው ቆይተዋል። በ2002 ምርጫ ወቅት ኢ/ር ሀይሉ ሻውል ይህን መመሪያ በመፈረማቸው ከፍተኛ የፖለቲካ ኪሳራ የደረሰባቸው ይመስለኛል፤ በወቅቱ አቶ ሃይሉ ፊርማውን የፈረሙት “ድጋሜ እንዳይታሰሩ ፈርተው ነው፣ ከፍተኛ ሀብት ያፈሰሱበትን ቢዝነስ እንዳይቀሙ በመስጋት ነው” እየተባሉ ይታሙ ነበር፤ ኢንጂነር ሃይሉ በገደምዳሜም ቢሆን፣ የአማካኙዋን ቦታ ይዘው ለመታገል ፈልገው ነበር። ኢ/ር ግዛቸውም ይህንን “የስነምግባር መመሪያ” ካልፈረሙ ከኢህአዴግ ጋር ቁጭ ብለው እንደማይነጋገሩ ያውቃሉ። ላለፉት 5 አመታት የስነ ምግባር መመሪያውን “አልፈርምም” ብሎ ጠንካራ አቋም ያራመደ ድርጅት፣ በአዲሱ አመራር አቋሙን እንደገና ለመፈተሽ ያሰበ ይመስላል። ፓርቲው መመሪያውን አልፈርምም በሚለው አቋሙ ከጸና ግን አዲሱ ሊቀመንበር ከኢህአዴግ ጋር ገንቢ ግንኙነት ለመመስረት የሚቸገሩ ይመስለኛል፣ ሌላ መንገድ አዘጋጅተው ከሆነ አላውቅም።
Andualem Aragie
ኢ/ር ግዛቸው በመሀል መንገድ ለመጓዝ ከመረጡ ከእርሳቸው በፊት በዚሁ መንገድ ተጉዘው የተሰባበሩ ፖለቲከኞች እጣ ፋንታ እንደሚገጥማቸው ለመናገር ነብይ መሆንን አይጠይቅም ፤ የፓርቲው ህልውና አደጋ ውስጥ መውደቁም አያጠራጥርም። የያዙት አላማ ለበጎም ይሁን ለክፉ፣ አዲሱ መንገዳቸው ከፍርሀት ጋር ሊያያዝባቸው እንደሚችል ጥርጥር የለውም። ለዚህ ማጠናከሪያ የሚሆኑ ምክንያቶች ደግሞ አሉ። ሊቀመንበሩ ቀደም ብሎ፣ ከሌሎች የቅንጅት መሪዎች ጋር ታስረው በነበረበት ጊዜ የፈረሙት የይቅርታ ሰነድ አለ። ሊቀመንበሩ ገዢውን ፓርቲ የሚያስከፋ ነገር ከተናገሩ ይህ ፋይል በማንኛውም ጊዜ እንደሚመዝባቸው ይታወቃል፤ እንደ አንዱዓለም አራጌ የታሰሩበትን ገመድ ለመበጠስና ራሳቸውን ነጻ ለማውጣት ምን ያክል ተዘጋጅተዋል የሚለውን ለመመለስ እቸገራለሁ፣ ከምርጫ 2002 ልምድ እንዳየሁት ግን የእስር ገመዳቸውን ለመበጠስ መዘጋጀታቸውን እጠራጠራለሁ። እንዲያውም የመሀሉን መንገድ አማራጭ ” የታሰሩበትን ገመድ ሳይበጥሱ፣ በገመዱም አጥብቀው ሳይታሰሩ ለመጓዝ ከመፈለግ የመጣ” ይመስለኛል። ፓርቲው ቀድሞውንም በረጅም ገመድ የታሰረን ሰው በመሪነት መምረጥ አልነበረትም፣ ከመረጠም ገመዱን ለመበጠስ የተዘጋጀ መሆን አለበት።
UDJ
የሊቀመንበሩ አካሄድ በእስር ላይ በሚገኙት አንዱለአም አራጌና ናትናኤል መኮንን ላይ ተጽእኖ ማሳደሩ አይቀርም፤ አንዱዓለም ከሚታወቅባቸው ባህሪዎች አንዱ በአቋሙ የሚጸናና ላመነበት ነገር ህይወቱን ለመስጠት የተዘጋጀ ሰው መሆኑ ነው፤ ደስ ሲለው ወዲህ፣ ደስ ሳይለው ወዲያ የሚረግጥ ሰው አይደለም። ፓርቲው ለስድስት አመታት የተጓዘበትን መንገድ ቀይሮ መሀል ላይ ለመቆም ከወሰነ ፣ አቋማቸውን ለማሳወቅ እድል በማያገኙት አንዱአለምና ናትናኤል ላይ የስነልቦና ተጽእኖ ማሳደሩ አይቀርም። አዲሱ መሪ ይህን ያሰቡት አይመስለኝም፣ ካሰቡበትም የእነ አንዱአለምን ሁኔታ ከግምት ያስገቡ አይመስለኝም፣ ከግምት ውስጥ አስገብተውት ከሆነም ፣ አንድ ነገር አስበዋል ማለት ነው። ለማንኛውም መጪው ጊዜ ለአንድነት ፓርቲ ፈተና የሚሆንበት ይመስለኛል።

ሃጫሉ ሁንዴሳ በቦስተን ድንቅ ናት ኢትዮጵያ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ ያቀረበው ዘፈን ቪድዮ

$
0
0

ባለፈው ቅዳሜ በቦስተን “ድንቅ ናት ኢትዮጵያ” የተሰኘ ትልቅ የሙዚቃ ኮንሰርት ተደርጎ ነበር። በዚህ ኮንሰርት ላይ የተለያዩ ኢትዮጵያውያን ድምፃውያን ሥራዎቻቸውን አቅርበዋል። ስንታየሁ ሂቦንጎ፣ ሃፍቶም ገብረሚካኤል፣ ጃምቦ ጆቴ፣ ፋሲል ደመወዝ፣ ትርሃስ ኮበሌ፣ ሃጫሉ ሁንዴሳ፣ ንጉሱ ታምራት፣ አቡሽ ዘለቀ፣ አብነት ግርማ (ትንሹ ጥላሁን)ና ደራሲና ገጣሚ በ እውቀቱ ስዩም በዚህ ድንቅ ናት ኢትዮጵያ ኮንሰርት ላይ ተሳትፈዋል። በዚህ ኮንሰርት ላይ ከቀረቡ ዘፈኖች መካከል ምሽቱን ያደመቀው የሃጫሉ ሁንዴሳን ዘፈን ከመድረክ ላይ ተቀርጾ ደርሶናል – ይካፈሉት። እውነትም ድንቅ ናት ኢትዮጵያ!

hachaluu hundesa

ታጋይ ክንፈ ሓደራ ማን ነበሩ?

$
0
0

kiflu hadera አቶ ክንፈ ሓደራ በትግራይ ክለተ ዓዉሎ አዉራጃ ጉድ ወረዳ ከአባቱ ፊታዉራሪ ሓደራ ገብረእግዚአብሔርና ከእናቱ ወይዘሮ ብልሃቱ ተላ በታኅሣስ 13 ቀን 1945 ዓ.ም ተወለደ። የ1ኛ ደረጃ ትምሕርቱን በዉቅሮ ከተማ ከተከታተለ በኋላ ፣ የ2ኛ ደረጃ ትምሕርቱን መቐለ በዓጼ ዮሐንስ ት/ቤት አጠናቋል።

አቶ ክንፈ ሓደራ በስደት ወደ ሱዳን ሔዶ ረጅም ጊዜ በትግል ካሳለፈ በኋላ ወደካናዳ በመምጣት፣ ከባለቤቱና ሁለት ልጆቹ ጋር በኦታዋ ከተማ ሲኖር በደረሰበት ድንገተኛ አደጋ ሕይወቱ አልፎ አስከሬኑ በተወለደባት፣በሚወዳትና በታገለላት አገሩ ኢትዮጵያ ዉስጥ አርፏል። በኦታዋ የኢቲዮ ካናዳዉያን የዴሞክራሲ መድረክም፣ በትጋቱ፣ በመልካም ሥነ ምግባሩና በረጅም ጊዜ ታጋይነቱ፣ በተለይም በኢትዮጵያ አንድነትና በሕዝቦቿ እኩልነት ላይ በጽኑ እምነቱ የሚታወቀዉን አቶ ክንፈ ሓደራን፣ በኦታዋ ከተማ፣ በኖቬምበር 13 ቀን 2013 ዓ.ም አስቦትና አክብሮት ዉሏል። በዚህ በብሮንሰን ማዕከል ውስጥ በተደረገው ታላቅ ዝግጅት ላይ፣ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች፣ ጓደኞቹ እንዲሁም የመድረኩ አባላትና ቤተሰቦቻቸዉ ተገኝተዋል። በዝግጅቱ ላይም፣ የመድረኩ ተወካዮች ለአቶ ክንፈ ያላቸውን አክብሮትና አድናቆት ገልጸዋል።በተጨማሪም፣ ዶክተር አረጋዊ በርሄና አቶ መኰንን ዘለለዉ በእስካይፕ ቀርበው ስለአቶ ክንፈ ጠንካራ ኢትዮጵያዊነት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። ከዚያም፣ መድረኩ ለዚያ ቅንና እውነተኛ የኢትዮጵያ ልጅ ክብር ለቤተሰቡ ያዘጋጀውን ስጦታ ለተወካዩ አበርክቷል።

ከዚህ ቀጥሎ ደግሞ፣ የአቶ ክንፈ ሓደራ አጭር የትግል ታሪክ ቀርቧል።

የታጋይ ክንፈ አርአያነት

ሞት ለሁሉም ፍጡር የሚዳረስ የተፈጥሮ ሕግጋት ቢሆንም የታጋይ ወንድማችን ኣቶ ክንፈ ሓደራን በድንገተኛ ሞት ምክንያት ከኛ መለየቱ ስንዘክር ጥልቅ ሓዘን ይሰማናል። ይሁን እንጂ አቶ ክንፈ ትቶልን የሄደው ትልቅ የትግል አሻራና በሳል ሰብአዊ ስነ‐ምግባር አሁንም ወደፊትም ከኛ ጋር ስለሚኖር ሞቱ የአካል እንጂ የመንፈስ ሊሆን አይችልም። ኣቶ ክንፈ ሓደራ ገና ከወጣት ዕድሜው ጀምሮ ከተበደለ ህዝብ ጎን በመቆም ለፍትህ፤ ለእኩልነትና ለዘላቂ ሰላም መታገል ዓላማዬ ብሎ የሚኖር ሰው ነበረ። ይህ ዓላማው ነበር ወደ ምድረ ሱዳን ኮብልሎ ትግሉን እንዲገፋበት ያስገደደው። እየታገለም ኖረ፣እየታገለም ዘለቀ። ጠልቀን ካየነው፣ እንደ ታጋይ ክንፈ ለክቡር ዓላማ የሚኖር ሰው ካለ በጣም ጥቂትና የታደለም ነው።

ህወሓት ተመስርቶ የትጥቅ ትግል እንደጀመረ ‐ ከ38 ዓመታት በፊት መሆኑ ነው ‐ ኣቶ ክንፈ ሱዳን አገር በስደት ላይ እያለ ለስደት ያበቃውን ጭቆና ለመታገል ሲል ህወሓትን ተቀላቀለ። በዚያው ጊዜ ህወሓት ገና ትግል ጀማሪ ሆኖ በሱዳን መንግስት እውቅና ያላገኘበትና ተደብቆ የሚታገልበት ወቅት በመኖሩ ኣቶ ክንፈም በህቡእ ትግሉ ተሰማርቶ ድርጅቱ የጠየቀውን ከባድ ሃላፊነት፤ በተለይ ደግሞ ስደተኛው ህዝብን የማደራጀት ውስብስብ ስራ ለማከናወን ተሰማርተዋል፣ ስራውንም በሚገባ ተወጥቶታል።

በዛን ወቅት ትግሉ የሚጠይቀው መስዋእትነት እየከፈለ በነበረበት ጊዜ፣ በኣመራር ደረጃ የነበሩ የድርጅቱ ወኪሎች በምግባረ‐ብልሹነት ይዘፈቁ ስለ ነበር፤ ይህንን በመቃወምና መፍትሄ ለመሻት ባደረገው ጥረት ለፍትህ የቆመው ኣቶ ክንፈ ነጋ ጠባ ከኣመራር ኣባላቱ ጋር መጋጨቱ ኣልቀረም። ግጭቱ ግን መለስተኛ ቅራኔ ነው ከሚል አመልካከቱ የተነሳ በድርጅቱ ውስጥ ሆኖ ሊፈታው ያላሰለሰ በሳል ትግል አድርገዋል። ይህ በዚህ እንዳለ ህወሓት የመገንጠልን ዓላማ የሚያቀነቅነው ማኒፌስቶ‐68 ኣንግቦ ድንገት ብቅ በማለቱ በኢትዮጵያ ኣንድነት ልባዊ እምነት ያለው ኣቶ ክንፈ ከህወሓት ጋር የነበረው ግንኙነት ከተራ ቅራኔነት አልፎ ጭራሽኑ እንዲያቃርጠው ተገደደ።

ትግሉም በሌላ መልክ መቀጠል አስፈላጊ ሆነበት።

በተመሳሳይ እምነት ህወሓትን ተቃውመው ከወጡት ከነ ዶክተር ሃይለ ኣፅብሃ ጋር በመሆን ዴሞክራሲያዊ ምንቅስቃስ ህዝቢ ትግራይ (ዴምህት) የተባለውን ንቅናቄ በመመስረት በኢትዮጵያ እኩልነታዊ ኣንድነት እውን ለማድረግ ትግሉን ቀጠለ። ሁሉጊዜ “ትግራይ ኢትዮጵያ ካልሆነ ሌላ ማን ሊሆን ነው” በማለት ህወሓት በወቅቱ ያራገበውን የመገንጠል ኣባዜ በልበ‐ሙሉነት ፊት ለፊት መቃወም ጀመረ።

ቆየት ብሎም ህወሓት ከውስጥም ከውጭም በደረሰበት ተቃውሞ የመገንጠል ማኒፌስቶውን ውድቅ ኣድርጌዋለሁ ቢልም ኣቶ ክንፈ ኣላመነውም፤ አልተቀበለውም። የህወሓት አስመሳይ ለውጥ ኣለማመኑና አለመቀበሉ፣ ያድርጅት አሁን ድረስ ከሚያራግበው ከፋፋይ አባዜ ጋር አያይዘን ስናገናዝበው የኣቶ ክንፈ ኣርቆ ተመልካችነቱና የዓላማው ጥልቀትነቱ የሚያንፀባርቅ ሆኖ እናገኘዋለን። ይህ በሳል ኣቁዋሙ በህወሓት ኣመራር ስላልተወደደለት፤ ይባስ ብሎም እንደጠላት ተቆጥሮ በሱዳን ሃገር እያል ብዙ ወከባና እንግልት ደርሶበታል።

ታጋይ ኣቶ ክንፈ የመገንጠል ጀብደኞችን ብቻ ሳይሆን የተቃወመው፣ ኢትዮጵያ ሃገራችንን ለኣያሌ ቀውሰ የዳረጋት ጭፍንና የተወላገደ ኣንድነት አራማጆችንም በመቃወም ከብዙ የኣድህሮት ሃይሎቸ ጋርም ተላትመዋል። በሳልና ፍትሃዊ ዓላማው ከተለያዩ ተቃዋሚ ግንባሮች ዓላማ ጋር ቢያጋፍጠውም፣ ኣቶ ክንፈ ከኢትዮጵያዊ መስመሩ ስንዝርም ይሁን ፍንክች ሳይል በፅናት መታገል የቻለ ትልቅ ኣርኣያ ነው።

ከብዙ ኣቅጣጫም ግፊት የነበረበት ታጋይ ኣቶ ክንፈ፣ ቀደም ብሎ እንደማንኛው ከሱዳን የተሰደደው ኢትዮጵያዊ ራቅ ወዳለ የስደት ሃገር መውጣት ይችል ነበር። ነገር ግን ለግል ህይወቱ ቅድሚያ ባለመስጠትና ብዙ ኣመታት ያስቆጠረ በውስጡ የታመቀው ልባዊ የፍትህ ፍላጎት እዛው በሱዳን ሃገሩ ድንበር ላይ ቆይቶ እንዲታገል ኣስገድዶታል። ሆኖም የህወሓት ቂመኛና የአፈና እጅ በምድረ ሱዳን እያንሰራራ በመምጣቱ፣ ከሌሎቹ የዴምህት ኣባላት ጋር ሆኖ ሱዳንን ለቆ መውጣትና ራቅ ብሎ መታገል ግድ ሆነበት። ለዚህ ነበር ካናዳ ድረስ የመጣው።

ኣቶ ክንፈ እዚህ ካናዳ ድረስ መጥቶም ኣርቆ ኣሳቢነቱና ለወገኑ ፍትህ ፈላጊነቱ የሚያንፀባርቅው ትግሉ ከትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር ጋር በመሆን እስከ ዕለተ ሞቱ ድረስ በጥልቀት ቀጥሎበታል። በኢትዮጵያዊነትና በኢትዮጵያዊያን መካከል ያሉት ተቃራኒ ኣመለካከቶች የፈጠሩት ስሜታዊ ትርምስ ምንም ሳይበግረው ድሮውን ለተለመው ዘላቂ‐ፍትሃዊና እኩልነታዊ ኣንድነት በየመድረኩ ሲታገል ኖሮዋል።

በቅርቡ እንደዚሁ በኢትዮጵያ የጋራ ትግል ሸንጎ ስር ከተደራጁት ወገኖቹ ጋር ሆኖ ህይወቱ በድንገት እስካለፈችበት ድረስ ኣበክሮ ሲታገል የነበረ ጀግና ታጋይ ነው።

ኣቶ ክንፈ ሃደራ በድንገት ቢለየንም መልካም ስነ‐ምግባሩ፣ የዓላማ ፅናትና ታጋይነቱ እንዲሁም ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ፍትህ ፈላጊነቱ ለሁላችን ኣርኣያ በመሆን ለዘለኣለሙ ይዘልቃል፣ እያልን ለመላው ቤተሰቡና ለትግል አጋሮቹ አርአያነቱን እንዲጎናጸፉ እንመኛለን።

አቶ ሌንጮ ለታ “ሃገር ቤት ገብተን በመታገል አዲስ ታሪክ እንሰራለን”አሉ

$
0
0

አቶ ሌንጮ ለታ “”ሃገር ቤት ገብተን በመታገል አዲስ ታሪክ እንሰራለን” አሉ (ዘ-ሐበሻ) ባለፈው ሳምንት ዘ-ሐበሻ በሰበር ዜና እወጃዋ “እነ ሌንጮ ለታ ኢትዮጵያ ሊገቡ ነው” ስትል መዘገቧ ይታወሳል። የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግምባር ሊቀመበር የሆኑት አቶ ሌንጮ ለታ ጀርመን ድምጽ ራድዮ ላይ ቀርበው “አዎ እውነት ነው ሃገር ቤት ገብተን ልንታገል” ነው ሲሉ አረጋግጠዋል። “ባለፉት 20 ዓመታት ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ ይህ ወሬ ይወራ ነበር ያሉት አቶ ሌንጮ በቃለምልልሳቸው “ኖርዌይ ተቀምጬ ምን አደርጋለሁ፤ እዚህ የሚደረግ ትግል የለም ስለዚህ ሃገር ቤት ገብተን ነው የምንታገለው” ብለዋል።

“ለኢትዮጵያ ህዝቦች አዲስ ራዕይ አለኝ” በሚል የተመሰረተው የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ህጋዊ መሰረት ያለው አገራዊ አንድነትን ለመመስረትና ለሁሉም የምትሆን ኢትዮጵያን ለማቅናት ሃገር ቤት በመግባት እንደሚታገል ይፋ አድርጓል።

አቶ ሌንጮ ለታ ከጀርመን ድምጽ ራድዮ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ “ከመንግስትም ሆነ ከተቃዋሚዎች ጋር ድርድር እንፈልጋለን” ያሉበትን ቃለ ምልልስ ያድምጡት፦

በሃገር እንግሊዝም ሆነ በኢትዮጵያና በመላው ዓለም ለምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች ሁሉ

$
0
0

london
ከርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ይህ መልዕክታችን ይድረሳችሁ።

በእንግሊዝ ሃገር የምትገኘውን የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን ከስደተኛው ሕዝብ ነጥቆ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ሥር ለማዋል የኢትዮጵያው መንግሥት (ወያኔ /ኢህአዲግ) እና ለንደን የሚገኘው ኤንባሲው ለአባ ግርማ ከበደና ለአቡነ እንጦስ ሙሉ ድጋፍና ትብብር እያደረገ ቀንና ሌሊት አብረው በመሥራት ላይ መሆናቸውን ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታተመው ዜና ቤተ ክርስቲያን የተባለ መጽሔት ይፋ አደረገ።

(ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ)

ይድረስ ለጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም፡ ማስረሻ ላይ የተፈፀመው በእርስዎ የበኩር ልጅ ዮሐና ላይ ቢፈፀም ምን ይሰማዎታል?

$
0
0

ይድረስ ለአቶኃይለማርያም ደሳለኝ እና ለኢህአዴግ አመራሮች!

ብስራት ወልደሚካኤል
afrosonb@gmail.com,
addismediab@gmail.com

በቅድሚያ የከበረ ሰላምታዬ በያላችሁበት ይድረሳችሁ፤ ምንም እንኳ እናንተ ብዙውን ሰላም እየነሳችሁ ብታስቸግሩም፡፡ ዛሬ ግን እስኪ በእናንተ እና በቤተሰባችሁ ላይ እንዳይፈፀም የምትፈልጉትን በሌላው ላይ ስላደረጋችሁት ከብዙው አንዲት እውነት ብቻ አንስቼ ልጠይቃችሁ ወደድሁ፡፡ የጥያቄው መልስ ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለህሊናችሁ፣ እናንተ በምትመሩት አስከፊ፣ አፋኝ እና ጨቋኝ ስርዓት ሰለባ ለሆኑ እንዲሁም አሁንም በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የተለመደውን እኩይ ተግባር ለምትፈፅሙባቸውና ለቤተሰቦቻችሁ ይሆን ዘንድም አበክሬ እጠይቃለሁ፡፡
hailemariam and Yohana hailemariam
ክቡር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እርስዎ ተወልደው ባደጉበት የደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ቦለሶ ሶሬ ወረዳ መዲና በሆነችው አረካ ከተማን መቼም የሚረሷት አይመስለኝም፡፡ እርስዎ አሁን የደረሱበት የይምሰልም ይሁን ተግባር የጠቅላይሚኒስትርነት በትረ ስልጣን ከመጨበጦ በፊት እዛው አረካ ከተማ አካባቢ እንደ አብዛኛው የሀገራችን ህዝብ በግብርና እርሻ ሙያ ዕየተዳደሩ ነው እንበል፡፡ ታዲያ በዚህ ሙያ ሳሉ ልክ አሁን እንዳሉት ባለትዳር እና የ3 ልጆች አባት ሆነው፤ እርስዎ በሚመሩት ኢህአዴግም ይሁን 24 ሰዓት በምትኮንኑት ደርግ ስርዓት አርዓያ “ሞዴል” አርሶ አደር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ተብለው የትውልደ ቀዬዎትን ወክለው በደቡብ ክልል መንግስት ቢሸለሙ ምን ይሰማዎታል? ያው ደስታ እንደሚሉኝ አልጠራጠርም፡፡

አለበለዚያም ገበሬ ሆኜ አላውቅም ካሉም፤ ያኔ አርባምንጭ የውሃ ቴክኖሎጂ ተቋም (የአሁኑ አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተመረቁበት ሲቪል ምህንድስና(Civil Engineering) አሊያም ከፊንላንድ በተመረቁበት የአካባቢ ንፅህና ምህንድስና(Sanitory Enegineering) እስተማሩና እያስተዳደሩ ሞዴል መምህር ተብለው በወቅቱ ገዥ ስርዓት ቁንጮዎች ቢሸለሙ ምን ይሰማዎታል? አሁንም ያው ደስታ ነው እንጂ ሀዘን ሊሉኝ አይችሉም፡፡ ምክንያቱም ማንም ሰው በሙያው ጥሮ ግሮ ላበረከተው አስተዋፅዖ እና ለሌሎች መልካም አርዓያ በመሆኑ የሚጠላ አይኖርምና፡፡ ይሄንን ምሳሌ ለራስዎ መቀበል ካልቻሉም ከቤተሰብዎ እጅግ መልካም ነው ብለው አብልጠው የሚወዱት ወንድምዎ ካሉም በእርስዎ ምትክ እርሳቸውን ተክተው እርስዎን በታዛቢነት ያስቀምጡ፤ ስሜቶንም ያሰላሱ፣ ይግለፁ፡፡

በሙያዎ ለብዙ ዓመታት ሰርተው ለሌሎች አርዓያ ተብለው ሽልማት፣ እውቅና እና ሙገሳ ከተሽጎደጎደልዎ 3 ወር ሳይሞላ፤ ከትዳር አጋርዎ ወ/ሮ ሮማን ተስፋዬ እና የበኩር ልጅዎን ተማሪ ዮሐና ኃይለማርያምን ጨምረው ከሌሎች ልጆቾ ጋር አምላኬ በሰላም አሳድረኝ ብለው ተቃቅፈው ተኝተው በሸለሞት አካል አሸባሪ ተብለው ሌሊት በቤትዎና በቤተሰብዎ ላይ በ 16 “የፀረ-ሽብር” ግብረ ኃይል የጥይት እሩመታ ሲሰሙስ ምን ይሰማዎታል? አሁን ልክ እንደቅድሙ ደስታ ሊሉኝ አይችሉም፡፡ በዚህ ብቻ ሳያበቃ እርስዎን በቤተሰብዎ ፊት በሸለሞት አካል በ 16 ግብረ ኃይል ሽፍታ ነው ተብለው በክብር አርፈው ከተኙበት ቤት በሚተኮሱ የጥይት ናዳዎች በቤተሰብዎ ፊት ህይወትዎ እስከወዲያኛው ቢያልፍ እና እንደው ግማሽ ነብስ የለም እንጂ በከፊል ድርጊቱን ቢታዘቡት ምን ይላሉ; ከእርስዎ በተጨማሪ ለፍተው ጥረው ግረው ያቆሟት ቤት፣ ያፈሯቸው ላሞች ፣በጎችና በሬዎች በማያውቁት ነገር የጥይት ናዳ ሲያርፍባቸውስ; ከላይ በተጠቀሱት ሳያበቃ ግብረ ኃይሉ አሁን የሰው ህክምና ሳይንስ የምታጠናው የበኩር ልጅዎ ተማሪ ዮሐና ሌሊቱን ገና በ8 ዓመቷ ከእቅፎ ተኝታ እርስዎ ሲገደሉ እርሷ የምትፅፍበት፣ አሊያም በትርፍ ጊዜዋ ከብቶች የምታግድበት ወይንም እንደሌሎች ህፃናት ከአቻዎቿ ጋር ለመጫወት የምትጠቀምበት የቀኝ እጇ ሙሉ ለሙሉ በጥይት ቢቆረጥስ ምን ይሰማዎታል? በዚህም ደስታ እንደማይሉኝ ግልፅ ነው፡፡ ልክ በውጊያ አውድማ እንዳለ ወታደር ከወላጆቿ እቅፍ ሳለች ቀኝ እጇ የተቆረጠችው ልጅ ስታድግስ ምን ይሰማት ይሆን? ፍርዱን ህሊና ላለው ሁሉ ልተወው፡፡

ልክ እንደ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በሌሎች የኢህአዴግ አመራሮች እና አባላት ላይ ተመሳሳይ ድርጊት ቢፈፀም ምን ይሰማችኋል; እናንተም ደስታ እንደማትሉኝ አልጠራጠርም፡፡ ይህንን ሁሉ የጠቀስኩት በማንም የሰው ሰብኣዊ የሰው ልጅ ላይ እንዲህ ዓይነት ዘግናኝ ድርጊት እንዲፈፀም ፈልጌ ይደለም፤ ይሄንንም አቶ ኃይለማርያምም ሆኑ ሌሎች ግብር አበሮእዎ በቅን ልቦና እንድትረዱልኝ እሻለሁ፡፡

ክቡርነትዎ፤ ከላይ ብእርስዎ የጠቀስኩት ምሳሌ በሌላ ኢትዮጵያዊ ላይ በእናንተ ስርዓት አመራር የተፈፀመ እውነተኛ ድርጊት መሆኑንን ከዚህ እንደሚከተለው በአጭሩ ልነግሮት እወዳለሁ፡፡

ጥቅምት 15 ቀን 2006 ዓ.ም. በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ዳባት ወረዳ አረቦር ቀበሌ ልዩ ቦታው ደቀፉቀር በሚባል ስፍራ ከሌሊቱ 12 ሰዓት ከነ መላው ቤተሰቦቻቸው አምላኬ በሰላም አሳድረኝ ብለው የተኙ፤በእነ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ስርዓት ሞዴል አርሶ አድር ተብለው የተሸለሙ ታታሪ ገበሬ አቶ ማስረሻ ጥላሁን በ 16 የፀረ ሽብር ግብረኃይል በተተኮሱ የጥይት ናዳዎች እዛው እቤታቸው ህይወታቸው አልፏል፡፡ የሚያሳዝነው ለግድያ የተላከው ግብረ ኃይል አቶ ማስረሻን ከገደሉ በኋላም በመኖሪያ ቤታቸው ላይ ተከታታይ የጥይት ናዳ በማውረድ ቤታቸውን የጥይት ጌጥ ሲያደርጉት ጥረው ግረው ያፈሯቸው ከብቶችንም ከመግደል እና ከማቁሰል አልቦዘኑም ነበር፡፡

የሚገርመው እንዴት የአንድ ሰው መኖሪያ ቤት የቀድሞ የአድዋ ወይም ባድመ፣…የውጊያ ስፍራ ሊመስል እንደቻለ ግልፅ አይደለም፡፡

ከላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ እጅግ የሚዘገንነው እና የሚያሳዝነው በተመሳሳይ ሰዓት የአቶ ማስረሻ ጥላሁን የ 8 ዓመት ልጅ ስለእናት ማስረሻ እዛው በሞት ከተነጠቀው ወላጅ አባቷ እና በፀረ ሽብር ግብረኃይል ከተሸበሩ ምስኪን ቤተሰቦቿ እቅፍ ሆና ሲነጋ ጥቅምት 16 ቀን 2006 ዓ.ም. ከአቻዎቿ ጋር ትምህርት ቤት ስለመሄድ እና ስለመጫወት ስታልም ብዙ ስራዎችን የምትሰራበት ቀኝ እጇ በግብረ ኃይሉ ጥይት ሙሉ ለሙሉ ተቆርጧል፡፡

አቶ ኃይለማርያም በእርስዎ እና በግብር አበርዎ የሚመራው ኢህአዴግ ሞዴል አርሶ አደር ያላችኋቸውን አቶ ማስረሻ ጥላሁንን በ 16 “የፀረ ሽብር” ግብረ ኃይል ለማስገደል በወረዳውና በዞኑ አመራሮች ሽፍታ ነው የሚል ለባለቤታቸውና በህይወት ለተረፉ ልጆቻቸው መልስ ተሰጥቶ ፍትህ እንጦርጦስ ገብቷል፤ ቀድሞም ቢሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ኢህአዴግ እስካለ ፍትህ እና ርትዕ ከማግኘት ሰማይ ቤት ደርሶ መመለስ የቀለለ ይመስል ሰው ተስፋ ቢቆርጥም፤ ለወጉም ቢሆን ፍርድ ቤት መኳተኑ አልቀረም፡፡ ነገር ግን እሮጣ ያልጠገበች፣ክፉና ደጉን የማታውቅና ቂም በቀል የሌለባት፣ ዓለማችንንም ይሁን ሀገራችንን ኸረ እንደውም አካባቢዋን በቅጡ ለይታ የማታውቅ የ 8 ዓመቷ ህፃን ስለእናት ማስረሻ ጥላሁንን ምን ብላችሁ ይን እጇ እንዲቆረጥ የተደረገው? ነው ወይስ ይህቺን ህፃንም ሽፍታ ነች ልትሉን ነው? ኸ…ረ…ረ..የፍትህ ያለህ፣…የህፃን ልጅ ያለህ፣…ቢያንስ ሰብዓዊነት እንኳ እንዴት ይሳናችኋል?

እስኪ አቶ ኃይለማርያም ስለእናት ማስረሻ ላይ የተፈፀመው በእርስዎ የበኩር ልጅ ዮሐና ኃይለማርያም ላይ ቢፈፀም ምን ይሰማዎታል? ስለ እናንተ ልጆች እንደምታስቡ ሁሉ ስለሌሎች ህፃናት ያላችሁ አስተሳሰብና አመለካከት ወይም ግንዛቤ የት ድረስ ነው? ዛሬ በዚህ ግፈኛ ስርዓት ቀኝ እጇ የተቆረጠው ስለእናት ማስረሻ ነገ እንደማንኛውም ልጅ አራሷን፣ ቤተሰቧን፣ ሀገሯን ብሎም የዓለምን ማኀበረሰብ ልታገለግል ምትችል፣ ብዙ ተስፋ የሰነቀች ነች፡፡

አሁን ግን ገና የ !ኛ ክፍል ትምህርቷን በጀመረች አንድ ወር ከአስር ቀን የመመህሮቿን የፊደል አጣጣል ትዕዛዝ የምትቀበልበት ቀኝ እጇ ገና ከጅምሩ ተቆርጧል፡፡ በዚህም ምክንያት ሰኞ ማክሰኞ እያለች ትምህርቷን መከታተል ሲገባት ፍትህ አጥታ ከምትኖርበት ዳባት ወረዳ፣ ሰሜን ጎንደር ዞን ከዚያም የአማራ ክልል ፍትህ ፅፈት ቤት እስከ ህፃናት ጉዳይ በጥይት ናዳዎች ከተረፉ ቤተሰቦቿ ጋር ፍትህን ፍለጋ እየተንከራተተች ትገኛለች፡፡

በአንፃሩ ደግሞ የአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ልጅ ዮሐና ኃይለማርያም በተደላደለ ሰላም፣ ጤናና እና ሁኔታ የህክምና ትምህርት ትከታተላለች፣ የብአዴኑ ሊቀመንበር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን ልጆችም የተሻለ ትምህርት ቤት ከዚሁ ደህ ህዝብ በሚገኝ ገንዘብ ይማራሉ፣ የአቶ በረከት ስምዖንን ፣ የዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ የአቶ ሙክታር ከድር፣ የነ ሀሰን ሽፋ፣ የነ ጌታቸው አሰፋ ፣ የነ አያሌው ጎበዜ፣ የነ ገዱ አንዳርጋቸው፣ የነ ግዛቱ አብዩ እና የሌሎች የኢህአዴግ ሹማምንት ልጆች በህዝብ ሃብት ተንደላቀው በተመቻቸ ሁኔታ ይማራሉ፡፡ የዳባት ወረዳ ነዋሪዋ ህፃን ስለ እናት ማስረሻ ደግሞ ለትምህርት ባልተመቻቸ ሁኑታ እንኳ የጀመረችውን ትምህርት እንዳትማር ቀወላጅ አባቷን በግፍ ከማጣቷ በተጨማሪ ቀኝ እጇን ተቆርጣ ፍትህን ፍለጋ ትኳትናለች፡፡

ታዲያ ክቡር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እና ሌሎች የኢህአዴግ ሹማምንት ሆይ፤ የምትመሩት ስርዓት በህፃናት ስም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ረብጣ ዶላሮችን እንደሚያገኝ የምትዘነጉት አይመስለኝም፡፡ ይሁን እንጂ በህፃናቱ ስም የሚመጣው እርዳታ ቢያንስ በአግባቡ ጥቅም ላይ መዋል ባይችል እንኳ ለምን አንዲትን ህፃን በፀረ-ሽብር ግብረኃይል በጥይት ለማስመታት ዋለ? በዚህች ህፃን ልጅ እና ወላጅ አባቷን ጨምሮ በቤተሰቦቿ ላይ የተፈፀመው ግፍ የት ድረስ ያስኬዳችኋል? ይህችን ደብዳቤ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ አቶ ኃለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ይህቺ ደብዳቤ ደረሳችሁ ሌሎች የኢህአዴግ አመራሮች ፤ ስለ ህፃናት ልጆቻችሁ፣ ስለ እናቶቻችሁ ፣ ስለሚስቶቻችሁ እና ስለራሳችሁ ብላችሁ የዚህቺን ህፃን እና ቤተሰቦች ጊዜ ሳትሰጡ ፍትህን ፍለጋ እየደከሙ ነውና ፍትህን ይሻሉ፡፡

እነ አቶ ኃለማርም ደሳለኝ የእውነት ከልብ አዝናችሁና እና ተሰነምቷችሁ ፍትህን መስጠት ከቻላችሁ የድርጊቱ ፈፃሚዎች ብዙ በምታወሩበት ኢቴቪና በሌሎች መድረኮች ሌሎች አመራሮችም ሆኑ ህዝብ እንዲማሩበት ጭምሩ ተገቢው ፍርድ በግልፅ በአደባባይ ሊሰጥ ይገባል፡፡ እዚህ ላይ የሴቶች እና ህፃነት ጉዳይ ቢሮዎች፣ አቃቤ ህግ፣ ጠበቆች ፣የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችና ሌሎች የሚመለከታችሁ አካላት የድርሻችሁን ትወጡ ዘንድ ተግባሩ የት አለ? ስል መልሳችሁን በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡

ታህሣሥ 2006 ዓ.ም. ተፃፈ

አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ

አንድነት ፓርቲን በተመለከተ መልስ ለኢሳቱ ፋሲል የኔአለም –ከግርማ ካሳ

$
0
0

የኢሳት ባልደረባ አቶ ፋሲል የኔአለም «የአንድነት ፓርቲ የመጪው ጊዜ ፈተና» በሚል ርእስ የጻፉትን ዘሃበሻ ድህረ ገጽ ላይ አነበብኩ። አቶ ፋሲል ጽሁፉን ያቀረቡት እንደ ግል አስተያየት እንደመሆኑ፣ ኢሳትን በዚህ ዉስጥ ጣልቃ አላስገባም። የአንድነት ፓርቲ አዲሱ ሊቀመንበር፣ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራዉ፣ አገር ዉስጥ ለሚታተመዉ ሪፖርተር ጋዜጣ ከሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የሚከተለዉን በመጥቀስ ነበር አቶ ፋሲል ጹሁፋቸውን የጀመሩት

«ከኢሕአዴግ ጋር ገንቢ ግንኙነት እንዲኖረን እፈልጋለሁ። ኢትዮጵያ ዉስጥ የጥላቻ ፖለቲካ ማብቃት አለበት። ኢሕአዴግ ተቃዋሚዎችን የሚያያቸው እንደ ጠላት ከዚያም አልፎ እንደሽብርተኛ ነዉ። በእኛም በኩል ኢሕአዴግን የምናየው እንደ አዉሬ ነዉ። ምናልባትም የሰራዉን ሥራ ሁሉ ዋጋ ያለመስጠት አለ። አንዳንድ ጊዜ ፖለቲካችን ኢሕአዴግን መቃወም ብቻ ሆኗል። ያ መቆም አለበት። ትልቁ ኳስ ያለው ኢሕአዴግ ዘንድ ነዉ። እኔ በበኩሌ ወደፊት በማደርገዉ እንቅስቃሴ ገንቢ ግንኙነት አድርገን ያለዉን የፖለቲካ ምህዳር ለሁላችንም አኩል መሆን አለበት» በማለት ነበር።

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም


«ይህ መንገድ (ኢንጂነር ግዛቸው በሪፖእርት የታናገሩት) ፣ ካልተሳሳትኩ ሶስተኛ መንገድ የሚባለዉና አቶ ልደቱ አያሌው የ1997 ምርጫ አጣብቂኝ በገባበት ወቅት አምጥተው የደነጎሩት፣ በሌላ አነጋገር መሃል ላይ መቆም የሚባለው የፖለቲካ አካሄድ ነዉ» ሲሉ የጻፉት አቶ ፋሲል፣ ከአገዛዙ ጋር እርቅና ሰላም ለመፍጠር ፍቃደኝነት መኖሩ፣ በአንዱዋለም አራጌና በናትናኤል መኮንን ላይ ተጽእኖ ሊያሳደር እንደሚችል ፣ የአንድነት ፓርቲም አደጋ ላይ እንደሚጥል የሚያመላክቱ ሃሳቦችን ለማሳየት የሞከሩ ይመስላል። የአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤም፣ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራዉን ሊቀመንበር አድርጎ በመምረጡ፣ ትክክል እንዳልሰራም አቶ ፋሲል ጠቆም ሳያደርጉንም አላለፉም።

እዚህ ጽሁፍ ላይ ስለ ኢንጂነር ግዛቸው ብዙ መጻፍ አልፈልግም። ኢንጂነሩን ከማንም በላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያውቃቸዋል። አብዛኞቹ ወጣቶች በሆኑበት ፣ ከክልሎች ሁሉ በተወጣጡ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት የተመረጡም ናቸው። በዲሞክራሲ የማምን እንደመሆኔም፣ አገር ቤት፣ ፊት ለፊት አፈናን እየተጋፈጡ ያሉ፣ የአንድነት ፓርቲ አባላት «እነዚህ ናቸው የሚመሩን !» ብለው የመረጡትን እደግፋለሁ። እቀበላለሁም።

አሁን ግን ኢንጂነሩ ለሪፖርተር ሰጡ በተባሉት ሃሳቦች ላይ፣ አንዳንድ አስተያየቶችን እንዳቀርብ ይፈቀድልኝ። አንድነት ፓርቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀመሮ፣ የአንድነት ፓርቲ፣ ከገዢዉ ፓርቲ ጋር፣ ችግሮችን በሰላምና በዉይይት ለመፍታት ሁልጊዜ ፍላጎት እንደነበረዉ፣ የአንድነትን እንቅስቃሴ በቅርበት የሚከታተሉትና በሚገባ የሚያውቁት ነዉ። ገዢው ፓርቲ የተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎችን እያስቀመጠ፣ ለዉይይት ፍቃደኛ አልሆነም እንጂ፣ አንድነት ሁልጊዜ ለዉይይት በሩን የከፈተ፣ ሰላማዊ ድርጅት ነዉ። ኢንጂነር ግዛቸው፣ የተናገሩት አዲስ አባባል አይደለም። አቶ ፋሲልንም ለምን እንዳስቆጣ አልገባኝም። የቀድሞ ሊቀመናብርት፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን፣ ዶር ነጋሶ ጊዳዳ ጠይቆ መረዳትም ይቻላል። (በነገራችን ላይ ኢንጂነር ግዛቸውን ከልደቱ አይሌው ፣ አንድነትን ከኢዴፓ ጋር የማገናኘቱ ነገር ትንሽ አስቆኛል። አቶ ልደቱ በቅርቡ በአዲስ አድማስ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ዙሪያና ስለ ኤዴፓ ሶስተኛ መንገድ ወደፊት በሰፊዉ እመለስበታለሁ)

አቶ አንዱዋለምን በተመለከተ አንድ ነገር ላንሳ። ይህ ወጣት የዴሞክራሲ ታጋይ፣ የሰላም ሰው ነዉ። ብሄራዊ እርቅ በአገራችን እንዲመጣ የሚፈልግና የሚመኝ ነዉ። ኢንጂነር ግዛቸው የተናገሩትን እርሱም ቢሆን ይናገረዉ ነበር። አንዱዋለም ለአላማው የጸና ሰው እንደሆነ ሁላችንም እናውቃለን። ነገር ግን ለአላማ መጽናት ማለት በጥላቻ መሞላት ማለት አይደለም። የገዢዉን ፓርቲ ተግባራት እንጂ አንዱዋለም የሚጠላው፣ አሳሪዎቹን እንደ ጠላት የሚያይ አይደለም። ልብ ገዝተው ወደ ቀናዉ መንገድ ከመጡ ከምንም በላይ የሚያስደስተው ያ ነዉ። ለዚህም ነዉ ቀድሞ የሕወሃት ከፍተኛ አመራር የነበሩ እንደ አቶ ስዬ ያሉ ወገኖች፣ ወደ አንድነት እንዲመጡ ትልቅ አስተዋጾ ካደረጉ ወገኖች መካከል አንዱ የነበረዉ። አንዱዋለም፣ ሰላምና እርቅ እንደማይፈልግና ግትር እንደሆነ ተደረጎ መቅረቡ ትልቅ ስህተት ከመሆኑም ባሻገር፣ ዜጎች አንዱዋለም አራጌ ያልሆነዉ እንደሆነ አድርጎ እንዲያስቡ የሚያደርግ ጎጂ አቀራረብ ነዉ።

GizachewShiferawየአንድነት መሪዎች ከአንዱዋለም ጋር በቅርበት ይገናኛሉ። በአንድነት ዉስጥ ያለዉን ሁኔታም አንዱዋለም ያውቃል። እሥር ቤት ባሉ፣ በነአንዱዋለም እና በዉጭ ባሉት አንድነቶች መካከል ልዩነት የለም። አቶ ፋሲል የሚያስታወሱ ከሆነ ፣ በአዲስ አበባ፣ በቀበና አንድነት፣ በጠራዉ በመቶ ሺሆች በተገኙበት ሰልፍ ላይ፣ ከእሥር ቤት የመጡ የነአንዱዋለም ደብዳቤዎች ተነበዉ ነበር። የመንፈሰና የአላማ አንድነት በአንድነቶች ዉስጥ እንዳለ የሚያሳይ ነዉ። ለዚህ ነዉ አቶ ፋሲል አንዱን የአንድነት አባል በአንድ ወገን፣ ሌላዉን በሌላ ወገን ማቅረባቸው ብዙ ያላስደሰተኝ።

ለሰላምና ለእርቅ በር መክፈት፣ ገዢውን ፓርቲ ለማነጋገር መፈለግ፣ ፍርሃት አይደለም፤ የሰለጠነ የፍቅር ፖለቲካ እንጂ። ስለፍርሃት ማወቅ ከተፈለገ፣ ያገር ቤቱን ትግል ሸሽተው፣ በዉጭ «ዘራፍ» የሚሉ፣ በእነ አቶ ፋሲልም ይደገፋሉ የሚባሉ፣ የአንዳንድ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችን ማነጋገሩ መልካም ሊሆን ይችላል። ኢንጂነር ግዛቸው እዚያው አገዛዙ አፍንጫ ሥር ሆነው እየታገሉ ያሉ ናቸው። ዉጭ ሆነን እርሳቸውን «ፈሪ» ማለት፣ ትንሽ የሚያስተዛዝብ መሰለኝ።

የአንድነት ፓርቲ በሚቀጥሉት ጥቂት ወራቶች በሶስት መስክ፣ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን ለማድረግ ዝግጅት ላይ እንዳለ በአንድነት ራዲዮ ኢንጂነር ግዛቸው ለማስረዳት ሞከረዋል። የመጀመሪያው የተበታተኑ የፖለቲካ ድርጅቶችን አሰባብሶ ጠንካራ ተቃዋሚ መመስረት ነዉ። የሕዝቡ ጥያቄ «ተባበሩ ወይንም ተሰባባበሩ» የሚል ነዉ። የህዝብን ጥያቄም አክብሮ፣ በዚህም ረገድ ንግግሮች ከአረና ትግራይና እና ከመኢአድ ጋር እየተደረጉ ናቸው። ውይይቱ ተሳክቶ መልካም ዜና እንሰማለት የሚል ተስፋ አለኝ።

ሁለተኛዉ ወደ ሕዝቡ ወርዶ የፖለቲካ ሥራ መስራት ነዉ። ከሰኔ 2005 እስከ መስከረም 2006 ዓ.ም ተደረጎ በነበረዉ የሚሊየሞች ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴ ወቅት፣ በደሴ፣ በጎንደር፣ በባህር ዳር፣ በመቀሌ፣ በአዲስ አበባ፣ በአዳም፣ በፍቼ፣ በባሌ/ሮቢ. በወላይታ ሶዳ፣ በአርባ ምንጭ ፣ በጂንካ …ሰላማዊ ሰልፎች ተደርገዋል። ሕዝቡ ድረስ ተኪዶ፣ በየበሩ እየተንኳኳ፣ ወረቀቶች እየታደሉ ሕዝቡ ለመብቱና ለነጻነቱ እንዲነሳ የመቀስቀስ ሥራ ተሰርቷል። ያኔ የተደረገዉ አይነት እንቅስቃሴ፣ በስፋት ፣ በተጠናከረ መልኩ፣ የሚሊየነሞች ድምጽ ለነጻነት ክፍል ሁለት፣ ሶስት በሚል ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ነዉ።

በሶስተኛ ደረጃ ደግሞ፣ አገዛዙ ፍቃደኛ ከሆነ፣ ያሉትን የፖለቲካ ችግሮች በሰላምና በዉይይት መፍታት ነዉ። ኢንጂነር ግዛቸው «ኢሕአዴግ ፍቃደኛ ካልሆነ፣ እጆቻችንን አጣምረን እንቀመጣለን» አላሉም። የአንድነት ፓርቲም ከአገዛዙ መመሪያ የሚቀበል ድርጅት አይደለም። የትም ቦታ ቢኬድ፣ ችግሮችን በሰላም መፍታት ከተቻለ፣ ጭንቅላት ያለው ሰው ሁሉ፣ የሚመርጠው መንገድ ያ ነዉ። እንጂነሩ ግልጽ አድርገዉታል። «ኳሷ ኢሕአዴግ ሜዳ ላይ ናት» ነዉ ያሉት። ኢሕአዴግ በሩን ከዘጋ፣ ለውይይት ፍቃደኛ ካልሆነ፣ የታሰሩ የሕሊና እሥረኞችን ካልፈታ፣ ትግሉ አይቋረጥም። ነጻነቱን እና መብቱን ሕዝቡ በልመና የሚያገኘው አይደለም። ታግሎ እንጂ።

አቶ ፋሲል ስለ ምርጫ ስነ-ምግባር ኮድም አንስተዋል። የምርጫ ስነምግባር ኮዱን ካልፈረሙ ኢሕአዴግ ሊያነጋግራቸው እንደማይፈልግ የገለጹት አቶ ፋሲል፣ ኮዱን አንድነት መፈረም እንደሚኖርበትም ይናገራሉ። እዚህ ላይ ትክክል ናቸው። ገዢዉ ፓርቲ ከነአቦነግ ጋር ያለምንም ችግር ሲደራደር፣ ከነአንድነተኖች ጋር ግን የምርጫ ስነ ምግባር መግባር ኮዱን ፈርሙ የሚል ቅድመ ሁኔታ በማስቀመጥ በሩን መዝጋቱን እናውቃለን።የምርጫ ስነ መግባር ኮዱን አንድነት ከፈረመ ደግሞ፣ እንደ ፈሪና ደካም ተቆጥሮ፣ የአንድነት ተቀባይነቱ እንደሚያሽቆለቁል አቶ ፋሲል ለመግለጽ ሞክረዋል። በዚህ ከርሳቸው ጋር ልዩነት አለኝ።

ጋዜጠኛ ፋሲል ምን ያህል ስለ ምርጫ ስነ-ምግባር ኮዱ ፣ እውቀት እንዳላቸው፣ ምን ያህልም እንዳነበቡት አላዉቅም። ኮዱ የአገሪቷ ሕግ ሆኖ የወጣ፣ አንድነትም ሆነ አገር ዉስጥ ያሉ ድርጅቶች ሁሉ የሚቀበሉት ነዉ። በኮዱ ያሉ አንቀጾች ከአንድነት መርሆዎችና እሴቶች ጋር የሚቃረኑ አይደሉም። በመርህ ደረጃ፣ በኮዱ በተካተቱት፣ ያኔም የአንድነት ፓርቲ ችግር አለነበረዉም። በኮዱ ዙሪያ የተነሱ ዉዝግቦች፣ የስነ ምግባር ኮዱ መጥፎ ሆኖ ሳይሆን፣ በሌሎች ተጨማሪ ሁለት ሰነዶች ላይ ለምን ንግግር አልተደረገም በሚል ነበር። ሕግ ሆኖ የወጣው የስነ ምግባር ኮዱ፣ የምርጫ ተወዳዳሪዎች ምን ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው የሚተነትን ነዉ። የምርጫ አስፈጻሚዉን (ምርጫ ቦርድ) እንዲሁም የምርጫ ታዛቢዎች ሊያደርጉት ስለሚገባዉ የሚተነትኑ ሌሎች ሁለት ሰነዶች ነበሩ። በነርሱ ላይም ስምምነት ለምን አልተደረገም የሚል ነበር ክርክሩ።

UDJአንድነት ያኔ በመድረክ ዉስጥ ሆኖ ነበር የሚደራደረዉ። መድረኩ፣ «ሶስቱንም ሰነዶች ተወያይተን በሶስቱም ላይ መፈረም ነው ያለብን» የሚል አቋም ያዘ። ከዚህም የተነሳ እራሱን ከድርድር አወጣ። ያ ዉሳኔ በኔ ግምት ስህተት ነበር። አንድነት የያኔዉን የመድረክ ስህተት መድገም ያለበትም አይመስለኝም። አንዱን ሰነድ ፈርሞ፤ በሌሎቹ ሁለት ላይ በሂደት መነጋገር ይቻላል ነበር እኮ። የአንድነት ፓርቲ በሕግ የወጣዉን እና የሚቀበለዉን የምርጫ ስነ-ምግባር ኮድ ቢፈርም፣ ከዚያም የተነሳ ከአገዛዙ ጋር የዉይይትን በር ማስከፈት ቢችል፣ ትልቅ ሥራ ነበር የሚሰራዉ። አንዳንዴ በትንሹም በትልቁም ማክረር ጥሩ አይመስለኝም። ከዋናዎቹና አብየት ከሆኑ ፕሮግራሞቻችን ጋር እስካልተጋጨ ድረስ፣ በሌሎች ማናቸዉም ጉዳዮች ዘንድ ፈረንጆች እንደሚሉት ፍሌክሲቢሊቲ ሊኖረን ይገባል።

በመጨረሻ ይሄን ብዬ ላጠቃል። የአንድነት ፓርቲ ይኸው ከተመሰረተ ጀምሮ ሶስት ጠቅላላ ጉባኤዎችን አድርጓል። በሶስቱ የተለያዩ ሊቀመናብርት ነዉ የተመረጡት። የግድ ሌላ ጠቅላላ ጉባኤ መደረግ የለበትም፤ በማናቸዉም ጊዜ ብሄራዊ ምክር ቤቱ ኢንጂነር ግዛቸውን ከሃላፊነታቸው ሊያነሳ ይችላል። ፓርቲዉን በትክክል የማይመሩ ከሆነ፣ አብዛኛዉ የአንድነት አባል ሳይደግፍ፣ ድርጅቱን በአንድ አቅጣጫ ሊወስዱት አይችሉም። ተጠያቂ ናቸውና። በመሆኑም «ከአሁን ለአሁን እንዲህ ይሆናል» የሚል መሰረት የሌለው ዉዥንብሩ ዉስጥ ባንገባ ጥሩ ነዉ። አንድ ሰው ገና ሥራ ሳይጀምር ወደ ትችት መሮጡ አግባብነት ያለውም አይመስለኝም። የአንድነት ፓርቲ ላይ ከወዲሁ ከማሟረት፣ ከዳር ሆኖ ጠጠር ከመወርወር ፣ ፓርቲዉ አገር ቤት የሚያደርጋቸውን እንቅስቅሴዎች መደገፍ ፣ ፓርቲው ሥራዉን የማይሰራ ከሆነ ደግም፣ እንደደገፍነዉም ያኔ መተቸት የአባት ነዉ።

እንግዲህ እነዚህ ጥያቄዎች ለአቶ ፋሲልም ሆነ ለተቀረዉ ኢትዮጵያ መጠየቅ እፈልጋለሁ። በኢትዮጵያ ሕዝብ ጉልበት እና አቅም እንተማመናለን ወይ ? የኢትዮጵያን ሕዝብ ከላይ እስከ ታች ማደራጀቱ ዋና የፖለቲካ ተግባር ነዉ እንላለን ወይ ? በአዲስ አበባ እና ክልሎች ሰላማዊ ሰልፎች፣ ህዝባዊ ስብሰባዎች በስፋት እንዲደረጉ፣ ህዝቡ በራሱ እንዲተማመን የማድረግ ሥራ፣ እንዲሰራ፣ በ547 ወረዳዎች ጊዜና ጉልበታቸውን ሰጥተው፣ ለመታሰር፣ ለመገደል ዝግጁ የሆኑ፣ ሕዝቡን የሚያደራጁ ታጋዮች በስፋት እንዲሰማሩ፣ ሕዝቡ ያነባቸው ዘንድ ፣ ጋዜጦች፣ የቅሰቀሳ ወረቀቶች በስፋት እንዲሰራጩ እንፈልጋለን ወይ? መልሳችን አዎን ከሆነ፣ ታዲያ የዚህ ጥረት አካል መሆን አይጠበቅብንም?


ኡስታዝ አቡበክር አህመድ በመኪና ሰው ገጭተህ አምልጠሃል በሚል በሃሰት ክስ ተመሰረተባቸው

$
0
0

ሳዲቅ አህመድ እንደዘገበው

ኡስታዝ አቡበክር አህመድ በመኪና ሰው ገጭተህ አምልጠሃል በሚል በሃሰት ክስ ተመሰረተባቸውየህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ላይ ፖሊስ በሃሰተኛ ወንጀል አዲስ ክስ እንደመሰረተባቸው ምንጮች አስታወቁ፡፡

ኡስታዝ አቡበከር አህመድ የፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ዛሬ ረቡዕ እንዲቀርቡ የተደረገ ሲሆን በ 2004 በመኪና ሰው ገጭተው አምልጠዋል በሚል ክስ እንደተመሰረተባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

ኡስታዝ አቡበክር አህመድ ፍርድ ቤት ከቀረቡ ቡሃላ አቃቤ ህጉ ክሱን ለፍርድ ቤቱ በንባብ ያሰማ ሲሆን ሀምሌ 8 2004 ላይ በተለምዶ ሶማሌ ተራ በሚባለው አካባቢ ላይ በንብረት እና በሰው ሂወት ላይ አደጋ ሊያስከትል በሚችል መልኩ ከተገቢው ፍጥነት በላይ አሽከርካሪውን በማሽከርከር በአንድ ሰው የእጁ አውራ ጣት ላይ የስብራት አደጋ አድርሰው ጥለውት ሄደዋል የሚል ክስ እንዳቀረበባቸው ተዘግቧል፡፡

ይህም ድርጊት ተፈፀመ የተባለው ሃምሌ 8 ቀን የደህንንንት ሃይሎች የኮሚቴውን አመራሮች ከመንገድ ላይ በማገት ወደ ሚፈልጉት ቦታ የብልግና ስድብ እየሰደቡ ይዘዋቸው በሚወስዱበት ሰአት መሆኑ ታውቋል፡፡ በዚህ ቀን መታቂያቸውን አናሳይም ያሉት ደህንነቶች ጋጠወጥ በሆነ መልኩ ብልግና እየተሳደቡ ለማገት ያደረጉትን ሙከራ በማክሸፍ ወደ ታላቁ አንዋር መስጂድ አምልጠው መግባታቸው ይታወሳል፡፡ በዚህ ወቅት ነው ሰው ገጭታችሁ አምልጠሃል በሚል በሃሰት ወንጀል የቀረረበባቸው፡፡

ኡስታዝ አበቡበከር አህመድ ከዚህ ቀደም በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የወንጀል መርማሪ ፖሊሶች ወደሳቸው በመሄድ ይህን ወንጀል ፈፅመዋል በሚል ቃላቸውን እንዲሰጡ ተጠይቀው የነበረ ሲሆን ኡስታዝ አቡበከርም የተባለውን ድርጊት አለመፈፀማቸውን በወቅቱ መኪና ሲያሽከረክሩ እንዳልነበር፣መኪናውም የሌላ ሰው እንደነበር እና በሹፌር ሲሄዱ እንደነበር ብሎም ከፊት ለፊት በነበረው የመኪና መቀመጫ ላይም ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ተቀምጠው እንዳልነበር እና በደህንነቶች ጋጠ ወጥ በሆነ መንገድ የእገታ ወንጀል ሲፈፅምባቸው ከወንጀል ድርጊቱ ማምለጣቸውን በዝርዝር ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡

ይህንንም በማስመለከት ዛሬ ፍርድ ቤት በቀረቡበት ሰአት ፍርድ ቤቱ ቃላቸውን ሰጥተው እንደሆነ ለማረጋገጥ የጠየቃቸው ሲሆን ኡስታዝ አቡበከር አህመድም ቃላቸውን መስጠታቸውን እና የዚህ አይነት ድርጊት በወቅቱ አለመፈፀሙን ብሎም የሚያውቁት ጉዳይ እንደሌለ አስረድተዋል፡፡

ፍርድ ቤቱም ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የሚባሉ አካላት ፍርድ ቤት መቅረባቸውን የጠየቀ ቢሆንም አለመገኘታቸው የተገለፀ ሲሆን ምስክር የተባለ አንድ ግለሰብ ብቻ ግን ችሎት የቀረበ ሲሆን ሁሉም ተሟልተው እንዲቀርቡ ለጥር 28 ቀነ ቀጠሮ እንደተሰጣቸው ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

ይህ ክስ ሆን ተብሎ የኡስታዝ አቡበከር አህመድን ፅናት ለመፈታተን እና ተስፋ ለማስቆረጥ ሆን ተብሎ የተደረገ ተግባር ሲሆን በተጨማሪም ኮሚቴው በእስር ላይ ሆነው ባወጡት መግለጫ በመበሳጨታቸው እና የተፈጠረው መነቃቃት ወደሌላ አቅጣጫ ሆን ተብሎ ለማስቀየስ መሆኑን ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

ለትውስታ
ኢቲቪ በአቡበከር ላይ ሃሰተኛ ቪድዮ ሰርቶ ከለቀቀ በኋላ በስህተት ኤዲት ያልተደረገውን ቪድዮ ለቆት እንደነበር ይታወሳል፤ በድጋሚ ይመልከቱት

አጋቾች በአስገድዶ መድፈር 4 ልጅ ያስወለዷት ኢትዮጵያዊት ወደ ሃገሯ ለመግባት በየመን እስር ቤት ትማቅቃለች

$
0
0

በግሩም ተ/ሃይማኖት (ጋዜጠኛ) – ከየመን

yemen በጤና ችግር ምክንያት ሁሌም መሄድ ባልችልም በሄድኩ ቁጥር ሁሌም አሳዛኝ ነገር ነው እየገጠመኝ ያለው፡፡ የበዓል እለት እስረኞችን ለማየት እና በዓልን ለእነሱ ምሳ ማብላት አስበን ኢሚግሬሸን እስር ቤት ሄድን፡፡ ካጋጠሙኝ አሰቃቂ ነገሮች አንዱ አራት ልጅ ይዛ ብርድ ላይ እያደረች ያለች ሴት አወራኋት፡፡ አማርኛ መናገር የማትቸል በመሆኑ አስተርጓሚ ማግኘትም ችግር ሆኖብናል፡፡ የመን ውስጥ ያሉት ህገ-ወጥ አጓጓዦች ስደተኞችን እያፈኑ አሰቃይተው ከቤተሰቦቻቸው ገንዘብ እንዲያስልኩ ያስደርጋሉ፡፡

እነዚህ አጋቾች ያገቷት አንዲት ኢትዮጵያዊት አንድ ልጅ ይዛ ነው ከሶማሊያ የተሻገረችው፡፡ ሶማሊያም አስገድዶ የመድፈር ሁኔታ ገጥሟት ወልዳ ነው የመን የገባችው፡፡ አሁን ደግሞ አግተው የያዟት ቦታ ሶስት ልጅ ወልዳለች፡፡ አራት በግዳጅ የመጡ ልጆች ይዛ ወደሀገር ልትገባ ነው፡፡
መጀመሪያ ልጆቹን እንዴት እንደያዘቻቸው ስላልገባኝ እና አራት መሆናቸውን አይቼ ስለሁኔታው ግርምት ጭሮብኝ ጠየኳት፡፡

‹‹..ባህሩን ስሻገር የያዘኩት እንዷን ልጅ ነበር፡፡ ሀረድ የሚባለው ቦታ የሚያግቱት አፋኞች ያዙን የደረሰብኝን ተወው፡፡ ለሶስት አመት ተኩል እዛው አፍነው አቆዩኝ፡፡ በዚህን ጊዜ ነው እነዚህን ሶስት ልጆች የወለድኩት፡፡ እንዲያውም ሁለቱ ልጆች በ11 ወር ነው የሚበላለጡት፡፡ አራስ ቤት እያለሁ ምንም እረፍት የለኝም ነበር፡፡…››

አንዷን ልጅ ሶማሊያ አግብተሽ ነው ወለድሻት? የኔ ጥያቄ ነበር፡፡
‹‹ እሷንም ሶማሊያ ውስጥ ተገድጄ በተደረገ ግንኙነት ነው የወለድኳት….›› ከዚህ በላይ መስማት አልቻልኩም፡፡ እንባም ተናነቀኝ….እስኪ የምትለውን ቪዲዮውን እዩት….

Sport: አርሰን ቬንገር እያደኗቸው ያሉት 5 ወጣት ተጫዋቾች

$
0
0

ከይርጋ አበበ

Arsene-wenger (1)አርሴን ቬንገር ቡድናቸው ማራኪ ጨዋታ ማሳየት ከቻለ ወይም የክለባቸው የፋይናንስ እንቅስቃሴ ጤናማ ከሆነ ለዋንጫ ደንታ የላቸውም እየተባሉ ይተቻሉ። ለክለባቸው ውጤታማነት የሚያስፈልጉ ተጫዋቾችን ለመግዛት አይደፍሩም። በተቃራኒው ክለባቸው ውስጥ የሚገኙትንና ደህና ዋጋ እንደሚያስገኙ የሚያስቧቸውን ተጫዋቾች ወደ ገበያ ሲያቀርቡ ዓይናቸውን አያሹም ይባላሉ። «ቬንገር ዘጠኝ ዓመት ከዋንጫ ጋር መለያየቱ የማያስጨንቀው ሰው ነው» እያሉ የስፖርት ተንታኞች ያብጠለጥሏቸዋል።

ሆኖም አርሴን ቬንገር ለሚሰነ ዝርባቸው ትችት መልስ ለመስጠት የሚመስልና እጅግ ውድ ዋጋ የወጣበትን ተጫዋች ዘንድሮ እንዲገዛ አድርገዋል። አሠልጣኙ ዘንድሮ ድንገት ሳይጠበቁ ጀርመናዊውን የኳስ ሊቅ ሜሱት ኦዚልን በ42 ነጥብ 5 ሚሊዮን ፓውንድ ወደ ክለባቸው አዘዋውረ ውታል። ለዚህ ጀርመናዊው ኮከብ ያወጡት ገንዘብ በፕሪሚየር ሊጉ ከተከናወኑ ዝውውሮች ሁሉ በትልቅነቱ ሁለተኛው ነው። ቬንገርም በድርጊታቸው ተኩራርተው «እኔ የክለቤን ደረጃ የሚመጥን ከሆነ ለምን መቶ ሚሊዮንስ አያወጣም» ሲሉ ተናገሩ።
ከኦዚል መፈረም በኋላ መነቃቃት ታይቶበት የነበረው ክለባቸው ግን ቀስ በቀስ መንሸራተት በመጀመሩ ክለባቸውን ይበልጥ ማጠናከር እንዳለባቸው አስበዋል። በተለይ በአንዳንድ ቦታዎች ላይ ያለባቸውን ክፍተት ለመድፈን ትኩረት ሰጥተው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን በክለባቸው ኦፊሴላዊ ድረ-ገጽ አስታውቀዋል።

አርሴን ቬንገር በተለይ የግቡን መስመር ለማግኘት የተቸገረውን ኦሊቨር ዥሩን ለማገዝ የሚችል ሁነኛ ፊት አውራሪና ከጀርመናዊው መለሎ ፔር ሜርትሳከር ውጭ የሚተማመኑበት የኋላ መስመር ተጫዋች በቡድናቸው ውስጥ ባለመኖሩ እነዚህን ቦታዎች ለመድፈን እንደሚንቀሳቀሱ ይጠበቃል። ለመሆኑ የቬንገርን ዓይን ያንከራተቱት ከዋክብት እነማን ናቸው?

5. ላርስ ቤንደር

አርሰን ቬንገር በቡድናቸው ውስጥ ማቲው ፍላሚኒ በቦታው ቢኖርም ለተከላካዮቻቸው ተጨማሪ ሽፋን የሚሰጥላቸው የአማካይ መስመር ተጫዋች አስፈልጓቸዋል። ለዚህም ዓይናቸውን ያሳረፉበት በጀርመናዊው የባየር ሊቨርኩሰን ወጣት አማካይ ላርስ ቤንደር ላይ ነው። ቬንገር ለዚህ መስመር የሚሆነው ተጫዋች ምርጫ ላይ ላርስ ቤንደርን የመጀመሪያ ምርጫቸው ባያደርጉትም፤ እርሱንም ቢሆን ለማገኘት እስከመጨረሻው እንደሚታገሉ ይጠበቃል።

4. አሌክሳንደር ፓቶ

ኢማኑኤል አዲባዮርና ሮቢን ቫንፐርሲ አርሴናልን ከለቀቁ በኋላ አርሴን ቬንገር የክለባቸውን ደጋፊዎች አንጀት የሚያርስ አጥቂ በክለባቸው ማየት አልቻሉም። በቅርቡ የቫንፐርሲን ቦታ ይተካሉ ተብለው ወደ ክለቡ የተዘዋወሩት ጀርመናዊው ሉካስ ፖዶሊስኪና ፈረንሳዊው ኦሊቨር ዥሩ የታሰቡትን ያህል መሆን አልቻሉም።

በተለይ ሉካስ ፖዶሊስኪ በተደጋጋሚ ጉዳት የሚያጋጥመው ከመሆኑ አኳያ ኦሊቨር ዥሩን በብቸኝነት እንዲጠቀሙ ተገድደዋል። ሆኖም አርሰን ቬንገር ከሀገራቸው ልጅ የሚፈልጉትን አገልግሎት ማግኘት እንዳልቻሉ ፍንጮች እየተነገረ ይገኛል። ለዚህም ይመስላል ለብራዚላዊው አሌክሳንደር ፓቶ ዝውውር በራቸውን ክፍት አድርገው የልጁን ወደ ለንደን ማምራት በጉጉት የሚጠባበቁት።

የቀድሞው የኤሲ ሚላን አጥቂ በአሁኑ ክለቡ ኮሮንቲያስ እያሳየ ያለውን ብቃት የተመለከቱት የአርሴናል ጎረቤቶች ቶተንሃም ሆትስፐርሶችም የልጁ ፈላጊ ሆነው መቅረባቸው ለአርሰን ቬንገር ዳገት ሳይሆንባቸው አይቀርም እየተባለ ነው።
የተጫዋቹን የአውሮፓ ኑሮ እንደገና ለማስጀመር የጓጉት አርሰን ቬንገር ግን ፈተናውን ተቋቁመው የክለባቸውን ማሊያ ያለብሱታል የሚሉ አስተያየቶችም መነገር ከጀመሩ ቆይተዋል።

3. ጁሊያን ድራክስለር

ወጣቱ የሻልካ 04 አማካይ መስመር ተጫዋች ድራክስለር ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተዘዋውሮ መጫወት ይፈልጋል።። አርሴናል ደግሞ የድራክስለር ፈላጊ መሆኑን ቬንገር ፍንጭ ሰጥተዋል። አስተያየት ሰጭዎች ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስፔናውያንና ፈረንሳውያን ተጫዋቾችን «በቃኝ» ያሉ የሚመስሉት አርሰን ቬንገር ፊታቸውን ወደ ጀርመናውያን ማዞራቸውን ተመልክተው የድራክስለር ማረፊያ የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ ፍላይ ኤምሬትስ መሆኑ አይቀርም እያሉ ነው።
የሻልካው መለሎ ተጫዋች ድራክስለር ቬንገር የሚፈልጉት ዓይነት ተጫዋች መሆኑና ወጣትነቱ ወደ ሰሜን ለንደን የሚያደርገው ጉዞ እንደሚሳካ የስፖርት ቤተሰቡ ከፍተኛ ግምት የሰጠው ትኩረት መሆኑን ዘገባው ጨምሮ ገልጿል።

2. አይካይ ጎንዶጋን

የአርሰን ቬንገር የአማካይ መስመር ላይ ተመራጭ ተጫዋች ቢኖር ይህ የ23 ዓመት ጀርመናዊ ወጣት ነው። ቬንገር በአማካይ ተከላካይ ቦታ ከማቲው ፍላሚኒ ውጭ የክለባቸውን ማሊያ ለብሶ ሲጫወት ሊያዩት የሚፈልጉት ይህን የቦሩሲያ ዶርትሞንድ ተጫዋች ነው። ተጫዋቹን ለማግኘትም የሚከፈለውን ሁሉ ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ጎንዶጋን በማንቸስተር ዩናይትድ ሳይቀር ፈላጊው በዝቷል። ተጫዋቹን በእጃቸው ለማስገባት ከባድ ፈተና እንደሚጠብቃቸው የተረዱት አርሴን ቬንገር ልጁን ለማማለል በክለባቸው ያሉትን ስድስት ጀርመናውያን እንደሚጠቀሙ ሲገለጽ፣ ለእናት ክለቡ ደግሞ አሳማኝ የዝውውር ሂሳብ ለመክፈል የሚያግዳቸው ምንም ምክንያት እንደሌለ በልበ ሙሉነት ይናገራሉ።
አርሰን ቬንገር በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጫወት ፍላጎቱ ከፍተኛ የሆነውን ጎንዶጋንን ወደ ክለባቸው አዘዋውረው ከሀገሩ ልጆች ጋር ማጫወት ይችሉ እንደሆነ ወደፊት የምናየው ይሆናል።

Karim-Benzema-Hairstyles-20131. ካሪም ቤንዜማ

ካሪም ቤንዜማ ፈረንሳዊ ነው። ይህ የሪያል ማድሪድ ግብ አነፍናፊ ተጫዋች የማይፈልገው ክለብ በምድረ አውሮፓ የለም። ቬንገርም የሀገራቸውን ልጅ በማድሪድ ያለውን ቆይታ እንዳልወደደው ተረድተዋል። በማድሪድ ያለው ቆይታ ቀስ በቀስ እየተነቃነቀ መምጣቱን ተከትሎ ተጫዋቹ የቤርናባውን መውጫ በሮች እየተመለከተ ይገኛል። አርሰን ቬንገርም ከፍተኛ የዝውውር ሂሳብ መድበው እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን የተለያዩ የመረጃ ምንጮች እየዘገቡት ነው።
የኦሊቨር ዥሩ ግብ የማግባት ችግር እየተባባሰ መሄድ ተስፋ ያስቆረጣቸው ቬንገር ችግራቸውን እንዲያቃልላቸው የሀገራቸውን ልጅ ወደ ኢምሬትስ ማዘዋወር የመጀመሪያ ግባቸው ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

ስደተኞችን እንደ መንግስት “የገቢ ርዕስ”ከማየት አባዜ ባሻገር –ከሙሼ ሰሙ

$
0
0

ከሙሼ ሰሙ

mushe semu በመጀመርያዎቹ ሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶችን አስመልክቶ ባረቀቀው ደንብ አንቀጽ 18 ላይ ስደተኞችን ወይም መጤዎችን ስለማፈናቀል ድንጋጌ አውጥቶ ነበር፡፡ ድንጋጌው እንደሚያትተው ከሆነ መጠነ ሰፊ በሆነ ደረጃ፣ ያለማመዛዘን፣ ልዩነት ሳያደርግ ሃይል በታከለበት ሁኔታ መጤዎችንና ስደተኞችን ማፈናቀል በሰብአዊ ፍጡር ላይ እንደተሰራ ከባድ ወንጀል ተቆጥሮ አባል ሃገራት በድርጊቱ ፈጻሚ መንግስታት ላይ የጋራ አቋም እንዲወስዱ ስምምነታቸውን የሚጠይቅ ነበር፡፡

ይህ የተባበሩት መንግስታት ደንብ የሁሉንም ሃገራት ይሁንታ በተለያየ ምክንያት ማግኝት ባይችልም፤ በዓለማችን ላይ ስደተኛ የሌለው ሃገር ከቶም ሊገኝ ስለማይችል በመርህ ደረጃ ሁሉም መንግስታት የሚስማሙበት ጉዳይ እንደሆነ ጥርጥር የለውም፡፡ የዓለማችን የመጎጎዣ ስርዓት እጅግ በመቀልጠፉና በመዘመኑ፣ የጉዞ ውጣ ውረዳችን ከቀናት ወደ ሰዓታት በመቀነሱ፣ መረጃዎች በስፋትና በጥልቀት በመናኘታቸው ምክንያት ዓለማችን ከመቼውም ጊዜ በላይ ጠባለች፡፡ በዚህም ምክንያት የተሻለ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ሕይወት ፍለጋ ቁጥራቸው ይብዛም ይነስ ዜጎቹ ለስደት የማይዳረጉበት ሃገር የለም፡፡ እንግሊዞች ሁለተኛ ሃገራችን ወደሚሏት አሜሪካ ተሰደው፣ ይሰራሉ፡፡ እስራኤሎች፣ የሳኡዲ አረቢያና የአውሮፓ ዜጎች ሳይቀሩ በየሃገሩ በመኖር ሕይወታቸውን ለማቃናት ብሎም ለሃገራቸው ለመትረፍና ከግፍና መከራ ለመሸሽ ይሰደዳሉ፡፡ ዛሬ ላይ ሲወሳ እውነት ሊመስል ባይችልም፤ አብዛኛዎቹ የመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት ነዋሪዎች ሕይወታቸውን የሚገፉት በስደተኛነት እንደነበረ እጅግ ቢርቅ ከአንድ ትውልድ የማይዘል ሃቅ መሆኑን መረዳት ያሻል፡፡
1604714_600436510028405_2111798139_n
መጠነ ሰፊ ማፈናቀል (Mass Deportation) በዓለምችን ላይ አዲስ ክስትት አይደለም፡፡ የሳሳንያው ስረወ መንግስትና የፐርዢያው ንጉስ ኮስራው/ሽራው/ 292,000 ባርያዎችንና ምርኮኞችን በጦርነት ካሸነፋት ሃገር አፈናቅሏል፡፡ አሜሪካኖች በየዓመቱ በአስር ሺህ የሚቆጠሩ የላቲን ዜግነት ያላቸውን ስደተኞች አስገዳጅነት በተቀላቀለበት መንገድ ወደ ትውልድ ሃገራቸው ታባርራለች፡፡ እስራኤሎች ቁጥር ስፍር የሌላቸው ፈለስጢናውያንን ከቤታቸውና ከቀያቸው ሲያፈናቅሉና ሲያሰድዱ ዘመናት ተቆጥሯል፡፡ እስከዛሬም ድረስ ፈለስጢናውያን ሃገር አልባ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡
በዓለም ታሪክ ከፈለስጢኖች ቀጥሎ በመጠነ ሰፊነቱና በአሰቃቂነቱ በተለይ ተጠቃሽ የሆነው ማሰደደና ማፈናቀል ቱርኮች በአርመኖች ላይ እ.ኤ.አ ከ1915 ጀምሮ በሶስት ተከታታይ ሂደት የፈጸሙት ማፈናቀል ነበር፡፡ በአንደኛው ዓለም ጦርነት ከጀርመንና ከኦስትሮ ሃንጌሪያውያን ጋር ያበረችው ኦቶማን ቱርክ እ.ኤ.አ በ1922 የደረሰባት አሳፋሪ ሽንፈትና ውድቀት ከአንድ ሚሊያን ለሚበልጡ አርመኖች ከቀያቸውና ከመንደራቸው ለመነቀልና ሃገር አላባ ሆነው የስደተኛ ሕይወት እንዲገፉ ምክንያት ሆኗል፡፡ በሃንጌሪ፣ በሎክስመበርግና በቤልጅየም የተፈጸሙ በርካታ ማሰደዶችና ማፈናቀሎች ሌሎች ተጠቃሽ ምሳሌዎች ናቸው፡፡

ሕጋዊ በሆነ መንገድም ሆነ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ወደ አንድ ሃገር የሚገቡ መጤዎችንና ስደተኞችን ወደ መጡበት ሃገር ማሳደድ ወይም ማፈናቀል (Mass Deportation) የሉዓላዊ ሃገራት ወይም መንግስታት የማይገሰስ መብት ነው፡፡ ከሞራል ሙግት ውጭ ምክንያት ሊጠየቅበት የሚችል አይደለም፡፡ ይህንን ስንል ግን ዜጎቹ የተሰደዱበት ሃገር መንግስት በዜጎቹ መሳደድና መፈናቀል ምክንያት የተከሰተውንና የሚከሰተውን ኢኮኖሚያና ማህበራዊ ቀውስ አስመልክቶ ሊነሳ የሚገባው ጥያቄ የለም ማለት አይደለም፡፡ አጠቃላይ የካሳ ጥያቄ አንዱ ነው፡፡ በተለይ ትኩረት ከሚሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ ቅድሚ የሚሰጠው ስደተኞቹ ከውርደትና ከመብት ረገጣ ከለላ የሚያገኙበትን ሁኔታ ማምቻቸት አንዱ ሲሆን ሌላው ተሰዳጆቹ ሃብት ንብረታቸውን ሳይነጠቅ እንዲሰናበቱ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ነው፡፡ ምክንያታዊ የሆነ መንግስት የዜጎቹ ውርደት የሃገር ውርደት መሆኑ ሊነገረው የሚገባ ጉዳይ አይደለም፡፡ ሃገር ያለ ዜጎቹ የሚዋረድበት ሌላ መገለጫ የለውም፡፡ ከዜጎች ውጭ ሃገር ማለት ድንጋይ፣ ተራራ ወይም መሬትና ወንዝ… ነው፡፡

በኢትዮጵያዊያን ስደተኖች ቁጥር ዙርያ ተጨባጭ መረጃ ማቅረብ ባይቻልም በዓለም ላይ በኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ምክንያቶች በየሃገሩ የተበተኑ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ቁጥራቸው በሚሊዮኖች እንደሚቆጠር ይነገራል፡፡ ምናልባትም
ኢትዮጵያዊ ስደተኛ የሌለበት ሃገር ማግኝት አዳጋች እንደሆነም በርካታ ለስራም በግል የሚጓዙ ኢትዮጵያዊያን ይናገራሉ፡፡ በተቃራኒው ግን ስደት እንደዚህ ርካሽ የሆነባት ኢትዮጵያ ደግሞ ለስደት የተዳረጉ ዜጎቿን እውቅና በመንሳት፣ ጥበቃናና ከለላ በመነፈገ አቻ የማይገኛላት ሃገር ነች፡፡ ዜጎቻችን ለስደት የዳረገው ኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ወይም የሰብአዊ መብት ጥሰት መንስኤ የሆኑ መሪዎቻችን በስደተኛ ዜጎቻችን ላይ የሚደርሱ ግፎችን አይቶተው እንዳለዩ ሰምተው እንዳልሰሙ መሆን መገለጫቸው ነው፡፡ ጫጫታው ገፋ ሲል ደግሞ የእብድ ገላጋይ ይመስል በስደተኞቹ ላይ ስም እየለጠፉ ለጥቃት ማጋለጥ ከአንዴም ሁለቴ የታዘብነው ፈተና ነው፡፡

በገዢዎቻችን ታሪክ ስደተኞች በመካድ፣ ከለላና ድጋፍ በመንፈግ በተለይ ኢህአዴግን የሚደርስበት የለም፡፡ ኢህአዴግ ከሽግግሩ ጊዜ ጀምሮ በኤርትራ መሬት በጦርነቱ ተሸንፈው ወደ የመን፣ ሱዳን ሊቢያና የመሳሰሉት ሃገራት የተሰደዱ ኢትዮጵያዊን ወታደሮችን እውቅና በመንሳት በርካታ ግፍና መከራን እንዲቀበሉ አድርጓል፡፡ ከጦር ቀጠናቸው ውጭ ኤርትራን የማያውቁ በርካታ ወታደሮቻችን በኤርትራ በረሃዎች ላይ ሰብሳቢና ተመልካች ማጣታቸው ሳይንስ ከሰው ፍጠሩ ያልተወለዱ ይመስል የቂም በቀል መወጣጫ ሲሆኑ ኢህአዴግ “ሃይ፣ ጉዳዩ በዓለም አቀፍ ሕግን ስርዓት ይዳኝ” ማለት ስላልፈለገ ዜጎቻችን የትም ባክው ቀርተዋል፡፡ ይበልጥ የሚያስደንቀው ደግሞ ዜጎቻችን “ለወረራ የዘመቱ የደርግ ወታደሮች” ናቸው በማለት የእብድ ገላጋይ ዱላውን በማቀበሉ ወታደሮቹ አይከፍሉ ዋጋ እንዲከፍሉ መንስኤም ሆኖ ነበር፡፡ ዛሬ የተረሳ ቢመስለም በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ታሪክ በአስከፊነታቸው ከሚብጠለጠሉት አሳዛኝ ግፎች ባልተናነሰ ደረጃ ጠባሳውን ጥሎ ያለፈ ሂደት ነበር፡፡

ደርግ በሽብር እየታገዘ እንደ እርድ ከብት ከእርሻ መሬታቸውና ከየትምህርት ቤቱ ያነዳቸው የድሃ አርሶ አደርና የከተሜ ልጆች በኤርትራ መሬት ላይ ለሽንፈት መዳረጋቸው ሳያንሰቸው ተጨማሪ ግፍና መከራ ይቀበሉ ዘንድ ኢህአዴጎች ከሻቢያ ጋር ሊመሳጠርባቸውም ባልተገባ እንደነበር ዛሬ ላይ ድርጅቱ የሚስተው አይመስለኝም፡፡ ጥርሳቸው እየተነቀለ፣ ንብረታቸውን እያተዘረፉ እርቃናቸውን ወደ መጡበት እንዲመለሱ በመደረጋቸው ቁትር ስፍር የሌላቸው ዜጎች በየበርሃውና ጥሻው ውስጥ ወድቀው ቀርተዋል፡፡ በኮንቴይነር ውስጥ እየታሸጉ በባርነት ጉልበታቸውን የተበዘበዙ ወታደሮች ቁጥር ማንም ሊገምተው ከሚችለው በላይ እንደሆነ የሚዘነጋ አይደለም፡፡
saudi
ጊዜ ማለፉ እንደማቀር የሚውቁ አብው ሲተርቱ “ለሕሊናህ መፈረድ ቢያቅት ለጊዜ ፈረድ ይላሉ፡፡ ዛሬ ላይ ያ ሁሉ አልፎ ለደረሰው ውጥንቅጥ ሁሉ መንስኤ የነበሩት አዝማች የደርግ ባለስልጣናት “ይቅርታን አግኝተው” መጽሐፍ ለመድረስና በኢህአዴግ መድረኮች እያተጋበዙ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ለመወያየትና ኢህአዴግን ለማማከር በቅተዋል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ እነዚህ ወጣቶች ባልቀሰቀሱትና ባልፈቀዱት ጦርነቱ ውስጥ ተማግደዋል፡፡ ብዙዎቹም ከሞት መንጋጋ ማምለጥ ቢችሉም “የደርግ ሰራዊት” ነበሩ በሚል ሰበብ ብቻ በዓለም አቀፍ ሕግ የተደነገገውንና ለጦር ምርኮኛ የሚገባውን ጥበቃና ከለላ ሳያገኙ በመቅረታቸው የቂም በቀል መወጣጫ ለመሆን ሆነዋል፡፡ ኢህአዴግ በወቅቱ ለሕሊናም ሆነ ለጊዜ ባለመፍረዱ ቢያንስ አዝማቾቻቸው በይቅርታ ሰበብ የተቋዳሱትን የእፎይታ ሕይወት እንኳን ለመቋደስ አልታደሉም፡፡ ከጥፋታቸውም ሆነ ከሕሊና ጸጸት ይድኑ ዘንድ እድል አላገኙም፡፡
ምክንያታቸው ሊዋጥልኝ ባይችልም ኢህአዴግን ለመከላከል ሲባል ብቻ ጉዳዮችን በቀላሉ ከማያጣፉት የኢህአዴግ ካድሬዎች የሚያነሱ ኢህአዴግ መንግስት አልነበረም የሚሉ መከራከርያዎች እንዳሉ እገምታለሁ፡፡ ችግሩ የሚነሳው ኢህአዴግ መንግስት ለመሆን መደላድሉን ያላመቻቸና እርካቡን ያልተቆናጠጠ በመሆኑ ነው አልነበረም፡፡ ችግሩ የርዕዮተ ዓለምና የአመለካከት ነው፡፡ ዛሬም የሳኡዲውን ሌሎችንም ስደተኞችን በሚመለከት ያለው ግንዛቤ ይህው ነው፡፡ ኢህአዴግ ፍላጎቱ ቢኖረው ኖሮ መንግስት መሆን ሆነ አለመሆኑ ሊገድበው ባልተገባ ነበር፡፡ ተደማጭነቱ ቢቀር እንኳ፤ ቢያንስ አቤቱታ በማሰማት ጉዳዩ እንዲታሰብብትና አጀንዳ እንዲሆን ግፊት ለማድረግ ከግለሰብ የላቀ አቅም ነበረው፡፡ ደርግ በትጥቅ ትግል ዘመን በሕዝቦች ላይ በሚያካሂደው ማሳደድ ምክንያት ቀላል የማይባል ህዝብን እየተቀበለና እያገዘ እጅግ አስከፊ ስደቶችንና ውጣ ውረዶችን ከሕዝብ ጋር ያሳለፈ ድርጅት ውሎ ሳይድር በዚህ ዓይነት ድርጊት ውስጥ እጁ ሲገኝ መመልከት ለትንታኔ የሚከብድ መሆኑ አጠራጣሪ አይደለም፡፡

በዚህ ጉዳይ የኢህአዴግ ሁነኛ ባሕሪ ለመደገም ተጨማሪ አስርት ዓመታትን መጠበቅ አላስፈለገም ነበር፡፡ “ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይለቅም” እንዲሉ በ1990 ዓ.ም ያልተጠበቀው የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ሲፈነዳ ነገሮች ይበልጥ ፍንትው ብለው ወጡ፡፡ የደርግ ወታደሮች በሚል ስም ገና ከጅምሩ ስደተኞችን ከለላ በመንፈግና እውቅና በመንሳት አዲስ ታሪክ ያሟሸው
ኢህአዴግ፣ በመቀጠል ሚናውን ከተመልካችነት ወደ ስደተኛ አባራሪነት (Mass Deportion) አሳድጎ ብቅ አለ፡፡ ለዝንተ ዓለም ኢትዮጵያ ውስጥ በመኖር ኢትዮጵያዊነታቸውን በሕግ የተቀዳጁ፤ ነገር ግን በደም ኤርትራዊ የነበሩ አባወራ፣ ሴት፣ ሕጻናት ወይም ሽማግሌ ሳይመርጥ በጅምላ በማፈስ እስር ቤት እያጎረ ሃብት ንብረታቸውን ለመሰብሰብ እንኳን በቂ ጊዜ ሳያገኙ ከኢትዮጵያ አባሯል፡፡ ኢህአዴግ በኤርትራዊያን ላይ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ሲፈጸም ሂደቱን ለመቀልበስም ያልቻለው ወይም ያልፈለገው በሌላ ምክንያት ሳይሆን እንደዚህ ዓይነት የማሳደድ ድርጊቶች በሌሎች ላይ ሲፈጸም ዝምታን የመረጠ ድርጅት በመሆኑ ነበር፡፡
ዛሬ ላይ ኢህአዴግ በስደተኞች ላይ የሚያሳየው ፍጹም የሆነ ቸልተኝነት መንስኤው ገጽታ ያበላሻሉ ከሚል ጥቅል ድምዳሜ እንደሚነሳ እገምታለሁ፡፡ በተለይ ደግሞ ወደ አረብ ሃገርት በድህነት ምክንያት ስራ ፍለጋ ለሚሰደዱ ዜጎች እውቅና መስጠት የልማት አጀንዳዬንና ያስመዘገብኩትን ኢኮኖሚያዊ እድገት ያጨልማል፣ በስራ ፈጠራና በልማት ተጠምጄ እያለሁ እነሱ በስደት በመጠመድ የችግሩን ስፋትና ጥልቀት ገሃድ ያወጣሉ የሚል ድብቅ ( የማይነገር) ሰበብ ስላለው እንደሆነ መገመት አያዳግትም፡፡ ኢህአዴግ ከነባራዊ ሁኔታው ተነስቶ ስደተኞቹ ከችግሩ ጥልቀትና ስፋት የተነሳ ከመሰደድ እንደማይቦዝኑ ያውቃል፡፡ በዚህም ምክንያት ድህነትን ከስሩ አድርቄዋለሁ ማለትና በድህንት ሰበብ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተሰደዋል ማለት ለፕሮፓጋንዳ አያመችም፡፡ ያለው አማራጭ ስደተኞቹ በሚሊየን ቢቆጠሩም በሰላሳ ሺዎች እየገደቡ እንደ ሳኡዲዎቹ ጉዳዩ ገንፍሎ ገሃድ እስኪወጣ ድረስ እውቅና መንሳት ብቻ ነው፡፡

በመካከለኛው ምስራቅ በተለይ በሳኡዲ አረቢያ፣ በኩዌትና በሊባኖስ በሌሎቹም ሃገራት የዜጎቻችን የአካል ክፍሎች (Organs) ባልሰለጠኑ የመንደር ሃኪሞች ስለት እየተሞሸለቀ ለቱጃር አረቦች ሲቸበቸቡ ኢህአዴግን ጨምሮ ሁላችንም ለመታዘብ ችለናል፡፡ ዜጎቻችን ከህንጻ ላይ እየተወረሩ ተነኳኩተው በቃሬዛ አሊያም ከተሸከርካሪ ወንበር ጋር ተቆራኝተው ያለ ካሳ አንደ አሮጌ እቃ ሲወረወሩ ተመልክተናል፡፡ በየመን፣ በሱማሌና በሊቢያ በረሃዎች ዜጎቻችን አይዋረዱ ውርደት ሲዋረዱና መሸሺያና መከለያ አጥተው ጦርነት ላይ እንደተማረኩ የዝሙት ባርያዎች (Sex Selave) በሰንሰለት እየታሰሩ የዝሙት ፍላጎት ማርኪያ ሆነዋል፡፡ ወንዶቹ በባርነት ሲያገለግሉ የተቀረጹ ዶክመንትሪ ፊልሞችን በዓለም ዓቀፍ መገናኛ ብዙሃን አማካኝነት በጋራ ተመልክተናል፡፡ በደርግ ስርዓት ጦርነትና የመልካም አስተዳደር እጦት ፤ የተቃና የኢኮኖሚ ፖሊሲ አለመኖርን የመብት ረገጣ ባደረሱቡን ፈተና ምክንያት ሰቆቃችን፣ እርዛታችንና ልመናችን ዓለምን እንዳላሰለቸ ሁሉ ዛሬ ደግሞ ስደታችንና የስደተኝነት ታሪካችን መንግስታዊ ከለላና ድጋፍ በመነፈጉ የዓለም መገናኛ ብዙሃን መጠቋቆሚያና መዘባበቻ እንድንሆን አድርጎናል፡፡

በዚህ መልኩ በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ የሚደርሰው የተናጠል ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ተባብሶና ገዝፎ ጭካኔ ወደ ተሞላበት መጠነ ሰፊ ማፈናቀልና ማሰደደ ሲሸጋገር ኢህአዴግ የጉዳዩ ባለቤት መሆኑን መቀበል ባለመፈለጉ እራሱን በታዛቢነት አስቀምጦ መክረሙ ቀጣዩ አሳዛኝ ትዕይንት ነበር፡፡ ኢህአዴግ በተለይ በስደተኛች ጉዳይ ዘንድሮም እንዳልተሻሻለ የሚያረጋግጠው፤ በኤርትራ መሬት ላይ በስደት ሲባክኑ የነበሩ ወታደሮችን “ወራሪ የደርግ ወታደር” ማለቱ ለጥቃት በር የከፈተ መሆኑን ዘንግቶ፤ ዛሬ ላይ ደግሞ ከሳኡዲ በግፍ ለተፈናቀሉ ዜጎቻችንን ሌላ ተቀጻላ ስም ለመስጠት አለመቦዘኑ ነበር፡፡ ኢህአዴግ ግፉ እንደተጀመረ ሰሞን እራሱን ከደሙ ንጹሕ ለማድረግ ያቀደ በመሆኑ “ሕገ ወጥ ስደተኞች” የሚል ተቀጽላ በመስጠት ለመከራቸውና ውጣ ወረዳቸው ጀርባውን መስጠቱ ይታወሳል፡፡

የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ስደተኞችን በመቀበሏ ትልቅ ስፍራ የሚሰጣትን የኢትዮጵያ ሃገራችን ስደተኞች የእስልምና መሰረት በሆነችው በሳኡዲ አረቢያ አምባገንን ፖሊሶች፣ ደህንነትና ሰራዊት አማካኝነት በጠራራ ጸሃይና በዓለም አቀፍ መገናኝ ብዙሃን ካሜራ ፊት አስነዋሪ ድርጊት ፈጽመውብናል፡፡ ሰብአዊ ክባራችንን አዋርደዋል፡፡ ዜጎቻችንን ገድለዋል፡፡ ሴቶቻችንን ደፍረዋል፡፡ ሃገራዊ ክብራችንን ተፈታትነዋል፡፡ ይህ ሁሉ ድርጊት በሳኡዲ አረቢያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ደጃፍ ስር መፈጸሙ ሌላ አሳፋሪ ጉዳይ ነው፡፡ ኢምባሲው በሩን ከፍቶ የዜጎቻችንን መከራ ለመቋደስ መድፈር ቢያቅተው አንኳን ብሶታቸወን ለመዳመጥ በሩን ገርበብ አድርጎ መታዘብ አልቻለም፡፡

ይልቁንም የኢምባሲው አባላት በዘመናዊ ፎቴ ላይ ተቀምጠው የዜጎቻችንን ግፉ በዲሽ እንደ ፊልም እየተመለከቱ መመሪያ ከመጠበቅ ያለፈ ሚና አልነበራቸውም፡፡ ኢምባሲው የስደተኞቹን ፓስፖርት ለማደስ የአባይ ቦንድ መዋጮ ካልከፈላችሁ በማለት ቁም ስቅል ሲያሳያቸው ከርሞ ከሰባት ወር ውጣ ውረድ በኃላ ፓስፓርታቸውን ሳያድስና ሕጋዊነታቸውን ሳያረጋግጥ በመቅረቱ ያ ሁሉ መዓት በዜጎቻችን ላይ ሊወርድ ችሏል፡፡ ይህ የተለመደው የኢህአዴግ ችግር መገለጫ በመሆኑ

ለዚህ የዜጎቻችን ፈተና የተጠየቀም ሆነ ኃላፊነት የወሰደ የለም፡፡ ሕዝባዊ ነኝ ለሚል ድርጅት በግብር ከፋይ ሕዝብ ወጭ ለሚያለግሉና ለሕዝብ ለማይቆሙ ጥቂት የኢምባሲ ሰራተኞችን ከላላ መሆኑና ከሕዝብ ቁጣ መሸሸጉ እንቆቅልሽ ከመሆን ሊዘል አይችልም፡፡

እርግጥ ነው የሳዑዲ መንግስት የስራ ፈቃድ የሌላቸውን ቀርቶ ፈቃድ ያላቸውን ስደተኞችም ቢሆኑ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ተገቢውን ካሳ ከፍሎና ንብረታቸውን እንዲሰበስቡ አደርጎ ባዘጋጀላቸው ትርንስፓርት ግፍና መንገላታት ሳይደርስባቸው ማሰናበት ይችላል፡፡ የሳኡዲ መንግስት ይህንን አድርጎ ቢሆን ኖሮ ጥያቂ ሊነሳበት ባልተገባ ነበር፡፡ ነገር ግን፤ ከላይ ለማንሳት እንደሞከርኩት የተፈጸመው ግፉ መስመሩን የሳተ እንደመሆኑ መጠን ኢህአዴግ ለስደተኞቹ ተቀጸላ ስም እየሰጠና ቁጥራቸውን እያወራረደ ለጥቃት ከማጋለጥና ከደሙ ንጹሕ ለመምስል ከመትጋት ይልቅ፤ በቂ ምክንያት ስለነበረው ቢያንስ ማፈናቀሉንና ማሰደዱን ማስቆም ባይችል እንኳ መፍትሔ ሊያገኙ በሚገባቸው በርካታ የዜጎነት ጉዳዮች ዙርያ ጥላ ከለላ በመሆኑ በሕጋዊ መድረኮች ሁሉ መሟገት ነበረበት የሚል ጽኑ እምነት አለኝ፡፡ ለዚህም ቢያንስ ቢያንስ እነዚህን መሰረታዊ ጉዳዮች ማከናወን ነበረበት፡፡

የመጀመርያውና ወሳኙ ጉዳይ ለዜጎቹ እውቅና መስጠትና ለክብር ዘብ መቆም ነበር፡፡ ሳኡዲዎች በዚህ ደረጃ ዜጎቻችንን ሰብአዊ ክብራቸውን እንዳያዋርዱ ለመከላከል ኢህአዴግ ከሳኡዲ መንግሰት ጋር በማንኛውንም ጉዳይ ጋር ለመነጋገር ዝግጁነቱን ቀድሞ በመግለጽ በዜጎቹ ጉዳይ ሃላፊነት የሚሰማውና የዜጎቹን ክብር ለመታደግ ግዴታውንና ኃላፊነቱን የሚወጣ መንግስት መሆኑን ማረጋገጥ ነበረበት፡፡ ስደተኞቹ ለዚህ ሁሉ ጥቃት ለመጋለጥ የቻለሁትም ይህ ባለመሆኑና ባለቤት፣ ተጠሪም ሆነ ወቃሽ የሌላቸው ተደርገው በመወሰዳቸው እንደሆነ መረዳት ይቻላል፡፡ ስደተኞች ኑሮ ስለደላቸውና ስለተረፋቸው እንዳልተሰደዱ ይታወቃል፡፡ በርካታዎቹ መሬታቸው ምርት መስጠት አቅቶት በማረጡ ምክንያት ሌላ የሕይወት መንገድን የመረጡ ናቸው፡፡ ይህንንም የስደት ሕይወት ለማሳካት ሃብት ንብረታቸውን ሽጠው ወይም ተበድረውና ተለቅተው ጉዞ የጀመሩ ናቸው፡፡ ፊታቸውን ወደ ሃገር ቤት አዙረው ለመመለስም መጀመርያ እዳ መክፈል የሚችሉ መሆናቸውን ማረጋገጥ ነበረባቸው፡፡ ቀጥሎም እዳቸውን መክፈል ቢችሉ ዳግም ወደ ችጋርና ሰቆቃ ሕይወት ላለመመለስ ትንሽም ብትሆን ጥሪት መቋጠር ነነበረባቸው፡፡ አብዛኛዎቹ ስደተኞቹ ይህንን ማቃናት ባለመቻላቸው ተይዘው ከመመለስ ይልቅ እራሳቸውን ከሕግ በመሰወር ለመደበቅና ለመሸሽ መሞከራቸው የግድ ነበር፡፡ ይህንን ውስብስብ ችግር ለሳኡዲ መንግሰት፣ የደህንነትና የፖሊስ ተቋማት ቀድሞ በማስረዳት በሕገ ወጥነት ተፈርጀው ግፍ እንዳይፈጸምባቸው መከላከል ይቻል ነበር ፡፡

ሁለተኛው አነሰም በዛ የጉልበታቸውን ዋጋ የማስከበር ጉዳይ ነው፡፡ በመጀመርያውንም ዜጎቻችን የተሰደዱት ሃብት ለማፋራት አቅደው በመሆኑ ሃብታቸውን የማሰባሰብ ጉዳይ ኢህአዴግ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነበር፡፡ እነዚህ ስደተኞች በሳኡዲ ኢኮኖሚ ውስጥ ርካሽ ጉልበታቸውን በመሸጥ ቀላል የማይባል አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው መገመት ይቻላል፡፡ በተለይ ደግሞ ማሰደዱ ሃይልና ግፍ የተቀላቀለበት በዘመቻ የተደረገ እንደመሆኑ መጠን ብዙዎቹ ያፈሯትን ጥሪት ለመሰብሰብና ደሞዛቸውን ለመቀበል እንኳን ፋታ አላገኙም፡፡ ስደተኞቹ ወደ ሃገር ተመልሰዋል፡፡ ሃብት ንብረታቸው ግን የትም ተዝረክርኮ ይገኛል፡፡ ሃብት ንብረታቸውን የማሰብሰብ ጉዳይ አሁንም ያልተፈታ ጥያቄ በመሆኑ ኢህአዴግ ዛሬም ላይ ሆኖ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ ኢህአዴግ ዓለም አቀፍ ግፊትና ተጽእኖ ፈጣሪ ተቋማትንና መንግስታትን መሰረት በማድረግ የሳኡዲን መንግስት ወደ ድርድር መውሰድ አለበት፡፡ ይህ ካልሆነም ጉዳይን ወደ ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት በመውሰድ ዜጎቻችን ተገቢውን ካሳ አንዲያገኙ ክስ በመመስረት ለዜጎቹ ጉዳይ ተጠሪና መንግስት መሆኑን በተግባር ማሳየት አለበት፡፡ ይህ እንቅስቃሴ ለስደተኞቹ ከሚያስገኘው ጥቅም በላይ ወደፊት ሌሎች መንግስታት በኢትዮጵያዊያን ላይ እንዲዚህ ዓይነት ድፍረት የተሞላበት ኢ-ሰብአዊ ድርጊት እንዳይፈጽሙ ተመክሮ ይሰጣል የሚል እምነት አለኝ፡፡

የሳኡዲ ስደተኞቹ ወደ ሃገራቸው ከመመለሳቸው ውጭ እዚህ ግባ የሚባል ተጨባጭ ስራ እየተሰራ እንዳልሆነ ለመገመት አያዳግትም፡፡ የሳኡዲ ስደተኞች ሕይወት ምናልባትም ከነበሩበት በባሰ ሁኔታ አስቸጋሪ ነገር ላይ እንደወደቀ የሚያሳዩ በርካታ ጠቋሚ ምልክቶች እያታዩ ነው፡፡ በቁጥር ቀላል የማያባሉት ወደ ቀያቸው ከመመለስ ይልቅ በየመንደሩ በሚገኙ ዝቅተኛ መኝታ ቤቶች አስርና አስራ አምስት እየሆኑ በደቦ መኖር ጀምረዋል፡፡ ሴቶች እህቶቻችን በሂደት ለምን አይነት ሕይወት እያተዘጋጁ እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ ወንዶቹ ዳግም በተለመደው መንገድ ወደ መጡበት ስደት ለመመለስ ጉልበትና አቅም እስኪፈጠር በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡ ለመሰንበት ሲባልም ወደ አስከፊ ሕይወት ማዝገማቸው የሚገመት ጉዳይ ነው፡፡

ችግሩ ሁሉንም ዜጋ ያስቆጣና በአንድ ያስተባበረ ጸጸትን የፈጠረ እንደነበር የሚረሳ አይደለም፡፡እንደተለመደው ጸጸቱ ቁጣ ከመቀስቀስ ውጭ ወደ ተግባራዊ እርምጃ መለወጥ አልቻለም፡፡ አጋጣሚው የቁጭትና የዋይታ ከመሆን አልፎ ለምን እንደዚህ ዓይነት ፈተና ላይ ወደቅን የሚል መሰረታዊ ጥያቄም ሊወልድ አልቻለም፡፡ ቀጥሉም በጥሞና ለመነጋገርም ሆነ መፍትሔ ለማመንጨት መንስኤና መንገድ ሊዘረጋ አልቻለም፡፡ የዲያስፖራ ፖለቲከኞችም የፖለቲካ ትኩሳቱን በማጋል ለሰልፍ ከመገባበዝ ውጭ የስደተኞቹን ሕይወት በቀጣይ ከአደጋ ለመታደግ ምን መደረግ አለበት ለማለት አልቻሉም፡፡ ዲያስፖራዎች “ከደማቁ ሰልፋቸው” በኃላ ጥቂት መዋጮ አድርገው፣ ቁጣቸውን አብርደው፤ አጀንዳቸውን በእንጥልጥል እጀመሩት ጉዳና ላይ ጥለውት መደ ጉዳያቸው ተመልሰዋል፡፡ ታዋቂ ሙዚቀኞች፣ ግለሰቦች፣ ባለሃብቶች አርቲስቶች… የኢቲቪን መድረክ ሲያጨናንቁ እንዳልነበረ ሁላ የስደተኞቹን ጉዳይ በቀጣይ ምን መፍትሔ ሊቸሩት እንዳቀዱ ለማሳየት አልደፈሩም፡፡ በእርግጥ መንግስት የጉዳዩ ቀዳሚው ባለቤት ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ መንግስት ፈተናውን ሊያልፍ አልቻለም፡፡ መንግሰት ፈተናውን ማለፍ ባለመቻሉ ዜጎቻችን አጋር የሌላቸውና ለዘለቄታው ከንቱና ተንከራታች ሆነው መቀረት አይገባቸውም፡፡
በአጠቃላይ ሂደቱ በአሳዛኝ መልኩ ቢጠናቀቅም፤ ከፍተኛ ትምህርት ሰጥቶ እንዳለፈ መረዳት ይቻላል፡፡ መንግስት የዜጎች ጉዳይ በሃገር ወስጥም ሆነ በወጭ ሃገር ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ነው፡፡ የትኩረት አቅጣጫው በመጀመርያ መሆን ያለበት ዜጎች በሃገራቸው ተጠቃሚ የሚሆኑበትንና መብታቸው የሚከበርበትን የመልካም አስተዳደርና የኢኮኖሚ ስርዓት በመዘርጋት ከስደትትና ከውርደት መታደግ ነው፡፡ በዚህ ሁሉ ሁኔታ አጣብቂኝም ውስጥ ሆነው ልባቸው በሕጋዊም ሆነ በሌላ መንገድ ለመሰደደ የተዘጋጁ ዜጎች መኖራቸው ስለማይቀር የስደተኞች ጉዳይ በአለም አቀፍ ግንኙታችን ላይ የምንመዘንበት አንዱ መገለጫችን በመሆኑ ዜጎቻችን ተገቢው ጥበቃና ከለላ እንዲያገኙ ማድረግ ያሻል፡፡ መንግስት፣ኢምባሲዎችና ቆንስላዎች በስደት ላይ የሚገኙ ዜጎቻችንን የገቢ ርዕስ አድርጎ ከማየት መታቀብ አለባቸው፡፡

Health: የብልት መጠናቸው አነስተኛ ለሆኑ ወንዶች 8 አማራጭ ህክምናዎች

$
0
0

ከማስረሻ አህመድ

ከአኗኗራችን፣ ከአመጋገባችን፣ ከአካባቢያችን እንዲሁም በሌሎች አያሌ ምክንያቶች የጤና እክል ይገጥመናል፡፡ እነዚህን እክሎች ደግሞ ለማስወገድ ወደየህክምና ማዕከሎች ጎራ ማለትና ህክምና ማግኘት የተለመደ ነው፡፡ ይሁን አንዳንድ የጤና እክሎችን አሣልፎ ለዶክተሮች መንገር እንዲሁም ማማከር በሀፍረት አልያም በሌላ ምክንያት ደብቀን መፍትሄ የማናገኘበት ደረጃ ተደርሶ ለአያሌ ጉዳቶች እንዳረጋለን፡፡ በዛሬው ጤና አምዳችን በመላው አለም የሚገኙ የወንዶቻችን ችግር ስለሆነው አነስተኛ የብልት መጠን ችግር ነው፡፡ እንደሚታወቀው ይህችግር ህክምና የሚያስፈልገው በውል የታወቀና ባይስተካከል ችግር የሚያስከትል እንከን ነው፡፡ በመሆኑም የዘረፉ ባለሞያዎች አነስተኛ የብልት መጠን ላላቸው ወንዶች የተለያዩ የመፍትሔ አማራጮችን መጠቀም እንደሚቻል ይመክራሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ የሚከተሉት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
men health
1. የሆርሞን ህክምና፡-

ይህ ቴስቴስትሮን የተባለውንና የወንዳወንድነት ባህሪ የሚያላብሰውን ሆርሞን በመርፌ መልክ በመስጠት የሚደረግ ህክምና ሲሆን ብዙውን ጊዜ በህፃንነት ሲሰጥ ውጤታማነቱ የጎላ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በጎልማሳነት ዕድሜ ላይ መውሰድ አናሳ ውጤታማነት ያለው ነው፡፡

2. ቀላል ዘዴ፡-

አንዳንድ ወንዶች ሰውነታቸው በመወፈሩ የተነሳ ጉያቸው (የብልታቸው አካባቢም) በትርፍ ስብ የሚሞላ ነው፡፡ ይህ መሆኑ የፍትዎት አካለ መጠኑ አንሶ እንዲታይ ያደርገዋል፡፡ በመሆኑም የሰውነት ክብደትን በመቀነስ ብቻ ከበፊቱ የተሻለ የብልት መጠን እንዲኖራቸው በቀላሉ ማድረግ ይችላሉ፡፡

3. መድሐኒቶች፡-

እነዚህ በሚዋጥና በቅባት መልክ ተዘጋጅተው የሚወሰዱ የህክምና ዘዴዎች ሲሆኑ የሚዘጋጁትም ከአንዳንድ ዕፅዋት ነው፡፡ በእነዚህ ዙሪያ የተደረጉ ጥናቶች እንዳስረገጡት ከሆነ መድሀኒቶቹ ውስጥ አንዳንድ ጎጆ በካይ ነገሮች ተገኝቶባቸዋል፡፡ መድሀኒቶቹን በኢንተርኔት በኩል ለሽያጭ የሚቀርቡ ናቸው፡፡

4. ፓምፕ፡-

ይህ በብልት ላይ የሚገጠም አነስተኛ መሳሪያ ሲሆን ትንሽዬ በእጅ የሚሰራ መዝውር ያለው ነው፡፡ ዋና አላማውም በብልት ውስጥ በ4 ያለ ደም እንዲገባ በማድረግ የብልትን ውጥረት በመጨመር መጠኑን ለመጨመር ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ይህ የሚሆነው በብልት ላይ የሚገጠመው መሳሪያ ‹‹ኔጌቲቪ ፕሬዠር›› በመፍጠር የመሳብ ሃይሉም ደምን ከደምስሮች ወደ ብልት ውስጥ በደንብ እንዲገባ ማድረግ ነው፡፡ ልክ ነዳጅን በቱቦ በኩል በአፉ ስቦ እንደማስተላለፉ ይቆጠራል የመዘውሩም ጥቅም ኔጌቲቭ ፕሬዥሩን ለመፍጠር ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ሁናቴ ማለትም የመሳብ ሀይሉ ከበዛ ወደ ብልት የሚገባው የደም መጠን በጣም ስለሚጨምር የብልትን ውስጣሚ ለስላሳ አካላት ላይ ጉዳት ሊያስከትልበት ስለሚችል የግፊት አጨማመሩ በፋብሪካው ትዕዛዝ መሰረት ብቻ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህፓምፕ አንዳንዶች ራስን በራስ ለማርካት ዘዴም ይጠቀሙበታል፡፡ በዚህ በኩል ለየት ያለ እውቅና ያተረፈው ደናልድ ቶምስን የተባለው ዳኛ ሲሆን በፍርድ ሂደት ወቅት ማሸኑን በመጠቀም ማስተርቤሽን ሲፈፅም ስለተደረሰበት የአራት አመት እስራት ተፈርዶበት በታሪክ ይዘከራል (እ.ኤ.አ ኦገስት 2006)፡፡ በተለይ በስሜት የመነቃቃት እና የመወጠር ችግር ላለበት ብልት የተዋጣለት ዘዴ ነው፡፡ እንዲሁም ቶሎ የመርካት ችግር ላለባቸው ወንዶችም በሰፊው ጠቀሜታን የሚሰጥ ነው፡፡ መሳሪያው ለረጅም ጊዜ ብልት እንደተወጠረ እንዲቆይ በሰፊው ጠቀሜታን የሚሰጥ ነው፡፡ መሳሪያው ለረጅም ጊዜ ብልት እንደተወጠረ እንዲቆይ የማድረግ ብቃት ያለው ነው፡፡ መሣሪያው በልዩ ስሙ ‹‹ቫኪውም ፓምፕ›› በመባል የሚታወቅ ነው፡፡

5. ተወጣሪ ተቀባሪዎች፡-

እነዚህ የህክምና አማራጮች (Inflatable implards) በመባል የሚጠሩ ሲሆኑ በብልት ውስጥ የሚቀበሩና ከፍተኛ የተለጣጭነት ባህሪ ያላቸው ቀጫጭን ቱቦዎች በቀላሉ በመግባትና እነሱን በመለጠጥ የብልትን የውጥረት መጠን መጨመር ነው፡፡ እንደአስፈላጊነቱ የቱቦዎቹ መጠን ተለቅ ተለቅ ያሉ ማድረግ የሚቻል ሲሆን ለረጅም ጊዜም ብልትን እንደተወጠረ የማቆየት ሀይል አላቸው፡፡ ቱቦዎቹ በብልት ውስጥ የሚቀበሩት በቀዶ ጥገና ሲሆን መጥፎ ነገር የተቀበሩትን ቱቦዎች መልሶ ማውጣት የማይቻል መሆኑ ሲሆን ባይወጡ ግን ጉዳት አያስከትልም፡፡

6. የማለብ ዘዴ፡-

ይህ ዘዴ ዋና ዓላማው በብልት ውስጥ የሚገባውን የደም መጠን በመጨመር የብልትን ውጥረት በሂደት የመጨመር ዘዴ ሲሆን የሚደረገውም በእጅ ጣቶች ነው፡፡ በከፊል የተነሳሳ ብልትን በአውራ ጣትና በሌባ ጣት ጠበቅ አድርጎ በመያዝ ወደ ላይ የመግፋት ሁኔታ ሲሆን አላማውም ደምን ወደ ብልት የማስገባት ሂደት ነው፡፡ ዘዴውም የብለትን ውስጣዊ የደም አቀባበል ውሃ የተነከረን ጨርቅ ከጣቶቹ ስር አብሮ በመጠቀም መከወን የበለጠ ውጤት እንዳለውም ይታወቃል፡፡

7. ክላምፒንግ፡-

ይህ ዘዴ ደግሞ በአንድ የተወጠረ ብልት- ታችኛው ስር አካባቢ ጠበቅ ባለ ቀለበት ወይም የጫማ ማሰሪያ ማሰር ነው፡፡ ብልቱን የሚያስሩት ቀለበት ወይም ክር ዓለማው ወደ ብልት የገባው ደም ወደ ኋላ እንዳይመለስና ብልት በደንብ እንደተወጠረ እንዲቆይ የሚያደርጉ ሲሆን ብልትን በሚገባ ማሸት ዘለቄታዊ ደም የመቀበል አቅሙንና መጠኑን እንዲጨምር ለማድረግም ነው፡፡

8. መለጠጥ፡-

ይህ ዘዴ እንደሚመክረው ከሆነ የብልትን ጫፉ (ክርክሩ አካባቢ) ቀጠን ባለ ገመድ ማሰርና ከዚያም ከገመድ ሌላኛው ጫፍ ከበድ ያለ ነገር በማንጠልጠል ረዘም ላሉ ደቂቃዎች ማቆየት ነው፡፡ ዓለማውም የብለትን የመለጠጥ አቅም ማጎልበት ነው፡፡ ይህም የሚሆነው የብልትን ውስጣዊ ተለጣጭ ክፍል ማለትም (ቱኒካ አልጂኒያን) የተባለውን ክፍል በመለጠጥ ሲሆን ዘዴውም ርዝመትን ብቻ ሳይሆን የውፍረት መጠንንም እንደሚጨምር ይታወቃል፡፡

ውድ አንባቢያን ምንም እንኳን ሁሉም ዘዴዎች መሉ በሙሉ ውጤታማ ናቸው ባይባልም የተወሰነ ለውጥ ግን የሚታይባቸው የህክምና ስልቶች ናቸው፡፡ ይሁን እንጅ ከራስ በራስ ዘዴዎቹ ባሻገር ያሉት የቀዶ ጥገና ህክምናዎችና መድሀኒቶች ብዙም አይመከሩም ፡፡ ምንም ከማድረግ በፊት ግን ሃኪምዎን ማማከርዎን እንዳይረሱ ዘ-ሐበሻ ትመክራለች።

የኢትዮጵያን ታሪክ ጥላሸት የመቀባት አባዜ –ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

$
0
0

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው ገዥው አካል በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ንጉስ የነበሩት የዳግማዊ አጼ ምኒልክ መቶኛ የሙት ዓመት በዚህ በያዝነው ዓመት (በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር) እየተከበረ ባለበት ወቅት ሙሉ ጊዜውን በመስጠት ንጉሱ የሰሩትን ታላቅ ስራ ሁሉ በማጣጣል እና ጥላሸት በመቀባት ዘመቻ ላይ በመጠመድ ታሪክ የማጠልሸት ድራማውን በመተወን ላይ ይገኛል፡፡ የታሪክ ማጠልሸት ዘመቻው በዋናነት እየተከናወነ ያለው ለገዥው አካል ቅርበት ባላቸው ታማኝ ሎሌዎች፣ የጥቅም ተጋሪዎች እና የእራሳቸው ስብዕና በሌላቸው አሻንጉሊቶች አማካይነት ነው፡፡ ገዥው አካል ሲያስነጥሰው መሃረብ ይዘው በሚቀርቡ አጎብዳጆቹ አማካይነት የጥላቻ መርዛማ ቃላትን፣ የሚቆጠቁጡ ባዶ ዲስኮሮችን እና እርባናየለሽ ምዕናባዊ ስዕል በአዕምሮው ላይ እየፈጠረ አጼ ምኒልክ የግዛት ማስፋፋት ጥማታቸውን ለማርካት ሲሉ በዜጎች ላይ የጭካኔ ተግባራትን እንደፈጸሙ በማስመሰል ለምንም የማይጠቅሙ እርባናየለሽ እና ተራ አሉባልታዎችን በማሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡
582717_198631520276500_222803186_n

የገዥው አካል ድንጉላ አገልጋዮች በማናቸውም የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች በመሰማራት ታሪካዊ ቅጥፈቶችን፣ አሳሳች ዘገባዎችን፣ የሀሰት ታሪክ ፈጠራዎችን፣ ሆን ተብሎ በሀሰት ላይ የተመሰረቱ መረጃዎችን እና ነጭ ውሸቶችን እንደ በቀቀን እየደጋገሙ በማሰራጨት ላይ ይገኛሉ፡፡ የዕኩይ ዓላማው አራማጆች በታላቁ የኢትዮጵያ መሪ ላይ ግነታዊ ኩምክና በመስራት፣ በማዋረድ እና እውነተኛውን ስብዕናቸውን ጥላሸት በመቀባት የስሜት ፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ውስጥ በመዘፈቅ ጌቶቻቸውን ለማስደሰት በታለመ ዕኩይ ምግባር ላይ ተጠምደው ይገኛሉ፡፡ የታላቁ መሪ ነብስ ከስጋቸው ከተለየች ከአንድ መቶ ዓመታት የጊዜ ቆይታ በኋላ የተቀበረን ጉዳይ በማንሳት ታላቁን መሪ ሰይጣናዊ ስብዕና እንደነበራቸው ለማስመሰል በማሰብ የዕኩይ ምግባር ጎተራዎቹ የቻሉትን ያህል ጥረት ለማድረግ ሞክረዋል፡፡ አቶ መለስ ዜናዊ በህይወት ከተለዩ ሁለት ዓመታት እንኳን ሳይሞላቸው የዕኩይ ምግባራት ቋቶቹ የኢትዮጵያ አዳኝ መልዓክ ሊያደርጓቸው ይፈልጋሉ፡፡

በአሁኑ ጊዜ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ላይ በተከፈተው የገፍ ወይም የኃይል የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ወይም ደግሞ የአጼ ምኒልክን የሙት መንፈስ ደጋግመው በማንሳት ፍጹም ጥላቻ እና የጥላቻ አመለካከት እንዲንሰራፋ በገዥው አካል ስልታዊ እና የተቀነባበረ ዘመቻ የማካሄድ አመክንዮ ለማንም ቢሆን ሊደንቅ አይገባም፡፡ ሀቁ አንድ እና አንድ ብቻ ነው፡፡ የኸውም የምኒልክን ስም ጥላሸት በመቀባት (ሰይጣናዊ ስብዕና በመስጠት) በሚሽከረከር ጉዳይ ላይ ብቻ የሚቆም ጉዳይ አይደለም፡፡ ነገር ግን በቅርቡ በህይወት የተለዩትን የገዥውን አካል የአለቆች ሁሉ አለቃ (Capo di tutti capi) አቶ መለስ ዜናዊን በመላዕክነት ቀብቶ ለማቅረብ የታቀደ ዕኩይ ምግባር ነው፡፡

ዳግማዊ ምኒልክን ጥላሸት የሚቀቡ ሙትመንፈሶች፣

minilikበዳግማዊ አጼ ምኒልክ ላይ እየተካሄደ ያለው ከፍተኛ ጥላሸት የመቀባት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ያነጣጠረው የኢትዮጵያን ታሪክ በመፋቅ በአቶ መለስ ዜናዊ የመላዕክነት የህይወት ታሪክ (የመላዕክነት ትረካ) በመተካት የታላቋን ሀገር ትክክለኛ ታሪክ እንደገና ለመጻፍ፣ አዛብቶ ለመጻፍ፣ ገልብጦ ለመጻፍ፣ አወዛግቦ ለመጻፍ፣ በመቀባባት የሚያምር አስመስሎ ለማቅረብ እና እውነተኛውን ታሪክ ለማስወገድ በመደረግ ላይ ያለ ከንቱ ሙከራ ነው፡፡ የአጼ ምኒልክን ታሪክ በመሰረዝ የዘመናችን የ”አፍሪካ ታላቁ መሪ” በማለት የመለስ ዜናዊን ታሪክ ለመጻፍ ይፈልጋሉ፡፡ በሀሰት እምነት ላይ በመመስረት መለስ “አዲሱ የአፍሪካ መሪ ዝርያ“፣ መለስ “የዴሞክራሲያዊ ልማታዊ መንግስት ቀያሽ”፣ መለስ “በዓለም አቀፋዊ የሙቀት እና የአየር ጸባይ ለውጥ የአፍሪካ ጠበቃ”፣ መለስ “ከጂ-8 እና ጂ-20 መሪዎች ጋር በመሆን ክርናቸውን የሚያሳዩ አፍሪካዊ መሪ”፣ መለስ “የቻይና-አፍሪካ የትብብር መድረክ የቤጂንግ ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ጉባኤ ሊቀመንበር”፣ መለስ የሶማሌ ጅሃዲስቶች እና አሸባሪዎች አስወጋጅ”… ተብለው ከእውነተኛ ስብዕናቸው ውጭ በሆነ መልኩ እንዲመለክባቸው ይፍልጋሉ፡:

የታላቁን መሪ የዳግማዊ ምኒልክን ስብዕና ጥላሸት በመቀባት አቶ መለስን ቅብዓ መልዓክ (የተቀባ መልዓክ) ለማድረግ ይፈልጋሉ፡፡ ለመሆኑ አጼ ምኒልክን ጥላሸት የሚቀቧቸው ለምንድን ነው? ምክንያቱም አጼ ምኒልክ በአመራር ጥበባቸው እና በትግላቸው ግጭትን በመፍጠር ሲናቆሩ ከነበሩት ባላባቶች፣ ለስልጣን ብቻ ከሚቋምጡ ከተለያዩ አካባቢያዊ ንጉሶች፣ ከተለያዩ ልዕልቶች የቅምጥል የአገዛዝ ስርዓት፣ እና ከጎጣዊ ምስለኔዎች የተበታተነ አገዛዝ በማላቀቅ ዘመናዊቷን የአፍሪካ ብሄር ታላቋን ኢትዮጵያን በመመስረታቸው ብቻ ነው፡፡ የዕኩይ ምግባር አራማጆች አጼ ምኒልክን ጥላሸት ይቀቧቸዋል፣ ምክንያቱም ምኒልክ ታላቆቹን የአውሮፓ ኢምፔሪያሊስት ኃያላን በጦር ሜዳ ውሎ በማሸነፍ አንጸባራቂ ድል በመቀዳጀት የኢትዮጵያን ዘለቄታዊ ነጻነት ያጎናጸፉ እና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ያስከበሩ ጀግና መሪ በመሆናቸው ነው፡፡ ጥላሸት ይቀቧቸዋል ምክንያቱም ምኒልክ እውነተኛ የአፍሪካ መሪ በመሆናቸው ነው፡፡ የአጼ ምኒልክን ስም በማጥፋት እና ለኢትዮጵያ ህዝብ ያበረከቱትን የውርስ ትሩፋታቸውን በማንቋሸሽ ለአቶ መለስ ክብር ለመስጠት እና ከእርሳቸው የሚገኘውን ውርስ ብጹዕ/ቅዱስ ለማድረግ ይፈልጋሉ፡፡

ገዥው አካል የአጼ ምኒልክን ታሪክ በእራሱ ታሪክ ለመተካት ይፈልጋል፡፡ አጼ ምኒልክ የባቡር ሀዲድ በመዘርጋት የመጀመሪያው አፍሪካዊ መሪ ነበሩ፡፡ ይህንን አንጸባራቂ ታሪክ በመለወጥ አቶ መለስ ረዥም፣ ቆንጆ እና ቀላል የባቡር ሀዲድ ሲስተም በኢትዮጵያ ለማምጣት የመጀመሪያው መሪ ነበሩ በማለት የታሪክ ባለቤትነት ሽሚያን ለማጎናጸፍ ይፈልጋሉ፡፡ አጼ ምኒልክ የስልክ እና የቴሌግራፍ አገልግሎትን በአፍሪካ አህጉር በማስተዋወቅ የመጀመሪያው አፍሪካዊ መሪ ነበሩ፡፡ እ.ኤ.አ በ1889 አሌክሳንደር ግራህም ቤል “የድምጽ መነጋገሪያ መሳሪያ” የፓተንት ዕውቅና ካገኙበት 13 ዓመታት በኋላ እና በአጼ ምኒልክ ቤተመንግስት የመጀመሪያው የስልክ መስመር በተዘረጋበት ጊዜ በቴክኖሎጂው ሁኔታ ጭንቀት ውስጥ ገብተው የነበሩት የቤተክህነት ሰዎች ይህ የሰይጣን ስራ ነው በማለት ንጉሱ እንዲያስወግዱት በጠየቋቸው ጊዜ አጼ ምኒልክ ለቴክኖሎጂው ጠቀሜታ ካላቸው ጽኑ እምነት አኳያ ሳያስወግዱት ቀርተዋል፡፡ በአስርት ዓመታት ጊዜ ውስጥ አጼ ምኒልክ አዲስ አበባን በምስራቅ ኢትዮጵያ ከምትገኘው የሀረር ከተማ ጋር የሚያገናኝ የስልክ መስመር በመዘርጋት መርቀው ከፈቱ፡፡ ያንን አንጸባራቂ ታሪክ ወደ ጎን በማለት የአሁኖቹ ገዥዎች በኢትዮጵያ ዘመናዊ የመገናኛ ቴክኖሎጂ ሲስተምን በኢትዮጵያ ያመጡ አቶ መለስ ዜናዊ እንደሆኑ አድርገው ያቀርባሉ፡፡ እውነታው ግን በተገላቢጦሽ በአፍሪካ የስልክ እና የቴሌግራፍ መስመር በመዘርጋት ግንባርቀደም የነበረችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ ከአፍሪካ በመጥፎ የተንቀሳቃሽ ስልክ እና የኢንተርኔት አግልግሎት አጠቃቀም ሳቢያ በመጨረሻው እረድፍ ላይ ትገኛለች፡፡ ባለፈው ሳምንት የዎል ስትሪት መጽሄት/Wall Street Journal እንደዘገበው በኢትዮጵያ ውስጥ አርሶ አደሮች የተንቀሳቃሽ ስልኮች ቢይዙም “ችግሩ የግንኙነት መስመር ለማግኘት ብዙ ማይሎችን (ኪሎሜትሮችን)መጓዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡“ በማለት የችግሩን አሳሳቢነት አመላክቷል፡፡ ኢትዮጵያ በመጥፎ የኢንተርኔት አገልግሎት አጠቃቀም ከአፍሪካ ከመጨረሻዎቹ ሀገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡

የዘመኑ ገዥዎቻችን አጼ ምኒልክ የሴቶችን ጡት ቆርጠው የሚጥሉ ጨካኝ ንጉስ እንደሆኑ አድርገው ታሪክን አዛብተው ለመጻፍ ይፈልጋሉ፡፡ ጨካኝነት ከተነሳ ዘንድ ከአቶ መለስ ዜናዊ የበለጠ ጨካኝ እና አረመኔ ይኖራልን? አቶ መለስ እራሳቸው እ.ኤ.አ በ2005 በተደረገው ሀገራዊ ምርጫ መጭበርበር ምክንያት ተቃውሟቸውን ለመግለጽ በወጡ ያልታጠቁ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ለአነጣጥሮ ተኳሽ ጦራቸው ትዕዛዝ በመስጠት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲገደሉ አድርገዋል፡፡ ይህንን እልቂት አስመልክቶ በእራሳቸው በአቶ መለስ ልዩ ትዕዛዝ ጉዳዩን እንዲያጣራ የተሰየመው የአጣሪ ኮሚሽን ምርመራውን አካሂዶ ባቀረበው ዘገባ መሰረት በአቶ መለስ ቀጥታ ትዕዛዝ እና ቁጥጥር አማካይነት የፖሊስ እና የደህንነት ኃይሎች በዕቅድ ተይዞ እና ሆን ተብሎ ታስቦበት 193 ሰላማዊ ሰዎች እንዲገደሉ እና ሌሎች 763 ሰዎች ደግሞ ከባድ ቁስለኛ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ እ.ኤ.አ በ2004 አቶ መለስ እራሳቸው ለታጣቂዎቻቸው ትዕዛዝ በመስጠት በምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላ 400 ሰላማዊ ዜጎች እንዲያልቁ አድርገዋል፡፡ ኦጋዴን እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የተካሄደውን የአየር ድብደባ እና መንደሮችን በማቃጠል የጥቃት ሰለባ ያደረገው ወንጀል የተፈጸመው በአቶ መለስ ስልጣን ልዩ ትዕዛዝ ነበር፡፡ በአቶ መለስ ትዕዛዝ በኦጋዴን ታጣቂ ኃይሎች ሴቶችን አስገድደው ደፍረዋል፣ መንደሮችን አቃጥለዋል፣ ህዝቡን በሽብር ቆፍን ውስጥ ለመሸበብ ሲባል “የመቀጣጫ ግድያዎችን” ማለትም በህዝብ ፊት በአደባባይ በስቅላት እንዲሁም ጭንቅላትን ቆርጦ የመጣል ወንጀሎች እንዲፈጸሙ ተደርጓል፡፡ የተባበሩት መንግስታት የሂዩማን ራይትስ ዎች ተሟጋች ዳይሬክተር/United Nations Advocacy Director for Human Rights Watch ስቴቭ ክራውሻው በኦጋዴን አካባቢ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ወንጀል “ትንሿ ዳርፉር” በማለት አመሳስለው ገልጸውታል፡፡
ገዥዎቻችን አጼ ምኒልክን የኦሮሞ ህዝቦች ጠላት እንደሆኑ አድርገው ታሪክን በመበረዝ የታሪክ ድሪቶ አቀነባብረው እንደገና የጎደፈ ታሪክ ለመጻፍ ይታትራሉ፡፡ አቶ መለስ በህይወት ቢኖሩ ኖሮ እሳቸው እና የዕኩይ ምግባር አጋሮቻቸው በኦሮሞ ህዝብ ላይ እስከ አሁን ድረስ ያልተነገረውን እና ለመናገር የሚዘገንነውን በሰው ልጆች ላይ የፈጸሙትን ወንጀል ወደ ፍትህ አደባባይ በማቅረብ እንዲታይ ለማድረግ ከበቂ በላይ መረጃዎች አሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ2012 ፍሪደም ሀውስ/Freedom House የተባለው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ባቀረበው ዘገባ መሰረት አቶ መለስ እና አገዛዛቸው በኦሮሞ ህዝብ ላይ ሰፊ የሆነ የአድልኦ እና የጭቆና መረብ በመዘርጋት ተግባራት ላይ ተጠምደው ቆይተዋል፡፡ አቶ መለስ የኦሮሞ ነጻነት ግንባርን እንቅስቃሴ በመገደብ ብዛት ያላቸው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የሚጠረጠሩ የድርጅቱን አባላት እና መሪዎችን ከህግ አግባብ ውጭ በቁጥጥር ስር በማዋል በማጎሪያ እስርቤት አስገብተው ሲያሰቃዩ ቆይተዋል፣ አሁንም በመሰቃየት ላይ ይገኛሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ2001 የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ስልጣናቸውን ሲለቁ እንደተናገሩት “ወደ 25,000 የሚሆኑ የኦሮሞ ህዝቦች ከኦሮሞ ህዝቦች ነጻነት ግንባር ጋር በተያያዘ የገዥው አካል ክስ ምክንያት በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች እና በአዲስ አበባ ከተማ እስር ቤቶች ታስረው በመማቀቅ ላይ ነበሩ፡፡” በማለት ይፋ አድርገዋል፡፡ የመለስ የትግል ጓድ እና የቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ስዬ አብርሃ በሚያስገርም ሁኔታ እንደተመለከቱት “ቃሊቲ እስር ቤት ኦሮምኛ ይናገራል፣ በዚሁ ግቢ በአንድ በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞችን በሚይዝ ካምፕ ውስጥ 99 በመቶ የሚሆኑት እስረኞች ኦሮሞዎች ናቸው፡፡ አብዛኞቹ እስረኞች ደግሞ የታሰሩበት ምክንያት ምን እንደሆነ አያውቁም፣ ሆኖም ግን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ተጠርጣሪ በመባል ዓመታትን በእስር ቤት በማስቆጠር ላይ ይገኛሉ፡፡“ በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡

Adwavictoryእ.ኤ.አ በ2006 ጂሃዲስቶች (አሸባሪዎች) የሶማሌን አገር ወረዋታል እና የሶማሌ መንግስት ጣልቃ ገብቸ ጂሃዲስቶችን እንዳስወጣለት “ጋብዞኛል” በሚል ተንኮልን ያዘለ ሰበብ ምክንያት አቶ መለስ በሶማሌ አገር ላይ ወረራ አካሂደዋል፡፡ አቶ መለስ በቴሌቪዥን ቀርበው እንዲህ ብለዋል፣ “የአገራችንን ሉዓዋላዊነት ለማስከበር እና በእስልምና ፍርድ ቤቶች ህብረት እና በሌሎች ጸረ ኢትዮጵያ ኃይሎች በመታገዝ የሚያደርሷቸውን ተደጋጋሚ አደጋዎች ለመግታት ሲባል የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ወዳልፈለገው ጦርነት እንዲገባ ተገድዷል፡፡“ በተመሳሳይ መልኩ በዴሴምበር 27 2006 የአቶ መለስ ሰራዊት እና ታንኮች የሞቃዲሾን ከተማ ወረሩ፡፡ እ.ኤ.አ በኦገስት 2007 የአቶ መለስ ሰራዊት በሶማሌ ውስጥ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ተገታ፣ በሰው ህይወት ላይ የደረሰው ኪሳራ አስደንጋጭ ነበር፡፡ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን የሶማሌ ዜጎች ህይወት የተቀጠፈ ሲሆን ከ870,000 በላይ የሚሆኑት ዜጎች ደግሞ ሞቃዲሾን ለቀው ለመሰደድ ተገደዋል፡፡ በ2006 በሞቃዲሾ ከተማ ወደ 1.2 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን ህዝብ ነበር፡፡ ከአቶ መለስ የሶማሌ ወረራ በኋላ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች “ከአፍሪካ በጣም አስቀያሚ አስከፊ የሰብአዊ መብት ሁኔታ ያለበት“ በማለት የሶማሌን የሰብአዊ መብት አያያዝ በተጨባጭ ገልጸውታል፡፡

አጼ ምኒልክ ከአውሮፓውያን ወራሪ ኃይሎች ጋር የመከላከል ጦርነትን በማካሄድ በድል አድራጊነት ተወጥተዋል፡፡ አጼ ሚኒልክ የአውሮፓ ኃያል ከሚባል አገር ጋር ጦርነት በማድረግ በጦር ሜዳ ድል አድርገው ወራሪው ኃይል በመጣበት እግሩ ጓዙን ጠቅልሎ እንደ ውሻ ጅራቱን በእግሮቹ መካከል ወትፎ እንዲመለስ በማድረግ በአፍሪካ ታሪክ የመጀመሪያው መሪ መሆናቸው የሚካድ ጉዳይ አይደለም፡፡ አጼ ምኒልክ ወራሪውን የኢጣልያንን ጦር አምባላጌ እና መቀሌ ላይ ድል አድርገዋል፡፡ እንዲሁም እ.ኤ.አ በ1896 አድዋ ላይ ወሳኙን ፍልሚያ በማድረግ የአድዋን ጦርነት በድል አድራጊነት ተወጥተዋል፡፡ “ኋላቀር አፍሪካውያን ጥቁሮች” ወታደሮች ኃያሉን የአውሮፓ ኢምፔሪያሊስት የጦር ኃይል ያሸንፋል የሚል እምነት በማንም አውሮፓዊ የተገመተ አልነበረም፡፡ አጼ ምኒልክ በዘመናዊ መሳሪያ ትጥቅ፣ በስልት እና በቁሳቁስ አቅርቦት በዘመኑ በጣም የተጎዱ መሪ ቢሆኑም ቅሉ የብሩህ አዕምሮ ባለቤት እና ወታደራዊ ስልት የሚያውቁ በመሆናቸው ውጊያውን በማካሄድ ጦርነቱን አሸንፈው በአንጸባራቂ ድል በመታጀብ የነጮችን የበላይነት እና አይበገሬነት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ በማስወገድ ለጥቁር ህዝቦች በአጠቃላይ ለአፍሪካውያን ደግሞ በተለይ የኩራት ፈርጥ ለመሆን በቅተዋል፡፡ ብዙ የአውሮፓ ኃያላን አገሮች አጼ ምኒልክን በማታለል እና በማጭበርበር ከኢትዮጵያ ግዛት ቆርሰው በመውሰድ ኢትዮጵያን ቅኝ ተገዥ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ1889 አጼ ምኒልክ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የሚገኙ ግዛቶችን አስመልክቶ ከኢጣሊያ መንግስት ጋር የውጫሌ ስምምነትን አጸደቁ፡፡ በውል ስምምነት ሰነዱ የኢጣሊያንኛው ትርጉም ከኢትዮጵያ የአማርኛ ትርጉም ጋር የማይመሳሰል መሆኑን አጼ ምኒልክ እንደተገነዘቡ እና ኢትዮጵያ በኢጣሊያን ጠባቂነት የሚለውን ሀረግ ሲመለከቱ የውል ስምምነቱን በማውገዝ አፈረሱት፡፡

የገዥው አካል አፈቀላጤዎች አቶ መለስ ኢትዮጵያ የአህጉሩ ታላቅ አገር እንድትሆን ጥረት ያደረጉ እና የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ መሪ እንደሆኑ በማድነቅ እና ስብዕናቸውን ከፍ ከፍ በማድረግ የአሁኑን የኢትዮጵያ ታሪክ ደልዘው በእርሳቸው ተተክቶ እንዲጻፍ ነው በመዋተት ላይ የሚገኙት፡፡ አቶ መለስ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት እና ሉዓላዊነት ያስከበሩ መሪ እንደሆኑ አድርገው ለማሳየት ይፈልጋሉ፡፡ እውነታው ግን የተገላቢጦሹን ያመላክታል፡፡ እ.ኤ.አ ከ1998-1999 ድረስ የባድሜን የግዛት ወሰን ለማስከበር በተካሄደው የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ጦርነት የአቶ መለስ ጦር የ80,000 ኢትዮጵያውያንን ህይወት ያለምንም ወታደራዊ ስልት በጭዳነት ለመስዋዕትነት ዳርጎ ወታደራዊ ድልን ተቀዳጅቶ ነበር፡፡ በወገኖቻችን የህይወት እና ንብረት መስዋዕትነት የተገኘውን ድል ሰራዊቱ ገና አጣጥሞ ሳይጠግብ የኢትዮጵያው መሪ አቶ መለስ ከመቅጽበት በመገለባበጥ ባድሜን በዓለም አቀፋዊ የስምምነት ውል በማስቀየድ ለኤርትራ መንግስት ቡራኬ ብለዋል፡፡ በምንም ዓይነት መልኩ በየትኛውም አገር አንድ ወታደራዊ ኃይል እጅግ ከባድ መስዋዕትነትን ከፍሎ ያገኘውን አንጸባራቂ ድል ለተሸናፊው ጠላቱ በፈቃደኝነት መልሶ የሰጠበት የጦርነት ታሪክ የለም፣ ተመዝግቦም አያውቅም፡፡ እ.ኤ.አ በ1991 ወታደራዊውን አምባገነን ደርግን በትጥቅ ትግል ካስወገዱ በኋላ በአሜሪካ መንግስት አደራዳሪነት የሽግግር ስምምነቱ በሚፈረምበት ወቅት እኒሁ የኢትዮጵያው መሪ አቶ መለስ በኤርትራ የወሰን ግዛት ዳርቻ ላይ የምትገኘውን ከቀይ ባህር ጋር በመግቢያ እና በመውጫነት ለኢትዮጵያ ህዝብ የባህር በር በመሆን አገልግሎት የምትሰጠውን የአሰብን ወደብ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት እንድትካለል የቀረበውን ሀሳብ አልቀበልም በማለት አሁንም በድጋሜ ለኤርትራ መንግስት ቡራኬ በመስጠት ይደልዎ ብለዋል፡፡ አቶ መለስ የኢትዮጵያን ግዛት ለባዕድ ኃይል በመስጠት ታላቋን አገር ወደብአልባ በማድረግ በፈጸሙት የአገር ክህደት ወንጀል ብቸኛው ተጠያቂ ናቸው፡፡ አሁንም ተከታታይነት ያለውን የትራጄዲ ድራማ በመቀጠል በሚስጥር በተደረጉ ስምምነቶች የይስሙላው ፓርላማ ለስሙ እንኳ መከረበት ሳይባል ምንም ሳይታሰብበት በጥድፊያ እኒሁ የኢትዮጵያው “መሪ” አሁንም የኢትዮጵያ አንጡራ ግዛት የሆነውን መሬት ለሱዳን መንግስት እንደ የገና ስጦታ የእጅ መንሻ ቡራኬ አድርገውታል፡፡ እኒሁ የኢትዮጵያው መሪ አቶ መለስ በድብቅ እና ታማኝነት በጎደለው መልኩ የአገሪቱን እጅግ በጣም ለም የሆነውን በሚሊዮኖች ሄክታር የሚቆጠር መሬት ዕዳቸውን እንኳ ውል ባለው መልክ ለመክፈል ለማይችሉ የአየር ባየር ጭልፊት ነጋዴዎች አሁንም ለእጅ መንሻ አቅርበዋል፡፡

አጼ ምኒልክ የኢትዮጵያን አንድነት በማጠናከር ዘመናዊ የመንግስት መዋቅር ዘርግተዋል፡፡ አቶ መለስ ግን ምዕናባዊ ዘመናዊነትን አምጥተዋል፡፡ አቶ መለስ ያለሐኪሞች እና መድኃኒት ሆስፒታል ገንብተዋል፡፡ በአንድ ወቅት ሐኪሞች አያስፈልጉንም በማለት በይፋ ተናግረዋል፡፡ ብቃት ያላቸው የዩኒቭርስቲ መምህራን እና ፕሮፌሰሮች፣ መጻህፍት፣ ቤተ መጻህፍት፣ ወይም ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ሳይኖር ዩኒቨርስቲዎችን ገንብተዋል፡፡ የመጸዳጃ ሲስተም የሌላቸውን ህንጻዎች ገንብተዋል፡፡ አጼ ምኒልክ ኢትዮጵያን የምዕራቡ ዓለም ስልጣኔ ትሩፋት ተቋዳሽ እንድትሆን አድርገዋል፡፡ አቶ መለስ “ልማታዊ መንግስት” የሚል እርባናየለሽ ህልዮት ከምስራቅ ኢስያ ሀገራት አምባገነኖች ኮርጀው በማምጣት ኢትዮጵያን ወደ ኋላ መልሰዋታል፡፡ እ.ኤ.አ በ1991 ስልጣን ከያዙ በኋላ አቶ መለስ ዘመናዊውን የኢትዮጵያ መንግስት አወቃቀር በማፈራረስ ወዲያውኑ አገሪቱን ክልል እየተባለ በሚጠራው ወይም የአፓርታይድ አይነት ባንቱስታንስ ወይም ክልሊስታንስ የተባለ የመከፋፈል ተልዕኮውን አጠናቀቀ፡፡ አቶ መለስ በሀሰት ላይ በመመስረት ባለሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ ዕድገት አስመዝግበናል፣ እና “ኢትዮጵያ ነዳጅ ወደ ውጭ ከማይልኩ የሰብ ሰሀራ አፍሪካ አገሮች መካከል ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የምታስመዘግብ አገር ናት” በማለት በሸፍጥ ለማሳመን በመወትወት ላይ ይገኛሉ፡፡ እውነታው ግን ኢትዮጵያ በዓለም ከሚገኙ የመጨረሻዎቹ ደኃ አገሮች ከመጨረሻው በሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ አገር መሆኗን “ኢትዮጵያ ለምንድን ነው ደኃ የሆነችው?” በማለት ቀደም ሲል ባዘጋጀሁት ትችቴ ላይ በግልጽ አስቀምጨዋለሁ፡፡

አጼ ምኒልክ የኢትዮጵያ “ህዳሴ” መሪ ነበሩ፡፡ አገራቸውን ለማጠናከር እና ዘመናዊ ለማድረግ ወሳኝ የሚባሉ እርምጃዎችን ወስደዋል፡፡ ለዘመናዊ ቴክኖሎጂ ልዩ ትኩረት በመስጠት ለአገራቸው አዲስ ዓይነት የግንኙነት ስርዓት እንዲዘረጋ አድርገዋል፡፡ አጼ ምኒልክ አገራቸው ኢትዮጵያ የስልክ እና የቴሌግራፍ እንዲሁም ዘመናዊ የፖስታ አገልግሎት ተጠቃሚ እንደትሆን አድርገዋል፡፡ አጼ ምኒልክ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ እንዲጀመር አድርገዋል፡፡ የመጀመሪያዋን በሞተር ኃይል የምትንቀሳቀስ አውቶሞቢል ወደ ሀገራቸው ያስገቡ አጼ ምኒልክ ናቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የማሪያ ቴሬዛ ገንዘብን የማይመች የገንዘብ መገበያያን በዚያን ዘመን በዓለም ገበያ ላይ በመገበያያነት አገልግሎት ስራ ላይ ይውሉ በነበሩ በመዳብ የወርቅ ቁራጭ የገንዘብ ሳንቲሞች በመተካት ዘመናዊ የገንዘብ ግብይትን በኢትዮጵያ አስጀምረዋል፡፡ አጼ ምኒልክ ከምንም ከማንም በላይ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ቅድሚያ ይሰጡ ነበር፡፡ አጼ ምኒልክ እ.ኤ.አ በ1894 ከጅቡቲ እስከ አዲስ አበባ የሚዘልቅ የባቡ ሀዲድ መስመር ለመዘርጋት ከፈረንሳይ መንግስት ጋር የስምምነት ውል ፈረሙ፡፡ በተመሳሳይ ዓመት የአውሮፓ ኃያላን አገሮች አፍሪካን እንደ ቅርጫ ስጋ የሚከፋፍለውን የአውሮፓ ቅኝገዥዎች የበርሊን ጉባኤን አካሄዱ፡፡ በዚያን ጊዜ ፈረንሳዮች የነበራቸውን ኃይል በመተማመን ከባቡር ሀዲዱ ጋር በተያያዘ መልኩ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለመዳፈር ሲሞክሩ አገር ወዳዱ መሪ ፈረንሳዮችን ጭጭ እንዲሉ አድርገው በ1906 የአገራቸውን ሉዓላዊነት ካስጠበቁ በኋላ ነው ቀዝቀዝ ማለት የጀመሩት ሐዲዱም መሰራት የቀጠለው ፡፡ እንግዲህ እንዲህ የነበረውን አንጸባራቂ ታሪክ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው ገዥው አካል የውሸት የአቶ መለስን ትረካ በማጉላት የህዳሴው መሪ፣ በአፍሪካ ታሪክ እስከ አሁን ድረስ ታይቶ የማይታወቅ የኤሌክትሪክ ኃይል ግድብ ገንቢ፣ የድልድዮች ገንቢ፣ የመንገዶች እና የባቡር ሀዲዶች… በማለት ታሪክን አዛብቶ ሸውራራ ታሪክ ለመጻፍ እየተውተረተረነው ያለው፡፡

አጼ ምኒልክ የፊውዳል መንግስታት የበላይ የነበሩ መሪ ነበሩ፡፡ በወቅቱ በአገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ በነበረበት ጊዜ ማድረግ የሚፈልጉትን ማድረግ የሚችሉ አፍሪካዊ መሪ ነበሩ፡፡ በእግዚአብሄር በአላህ ፈቃድ አንዲት የተባበረች እና የተከበረች ኢትዮጵያን ለተተኪው ትውልድ አውርሰው አልፈዋል፡፡ የአቶ መለስ ጠንካራው የውርሳቸው ትሩፋት በአፍሪካ የመጀመሪያውን ፈላጭ ቆራጭ አምባገነናዊ አገዛዝ ማውረሳቸው ነው፡፡ በሁፊንግተን ፖስት ትችቴ/Huffington Post Commentary በግልጽ እንዳስቀመጥኩት “ዴሞክራሲ የህዝብ፣ በህዝብ፣ ለህዝብ የቆመ የመንግስት አስተዳደር ከሆነ የማፊያ አገዛዝ/thugocracy ደግሞ (የወሮ በላ) የሌቦች፣ ለሌቦች በሌቦች የቆመ የወሮ በላ መንግስት አስተዳደር ነው፡፡“ በግልጽ አባባል የማፊያ አገዛዝ የሚሽከረከረው በወሮበላ ሌቦች እና በዘራፊዎች ነው፡፡ በማፊያ የአገዛዝ ስርዓት የፖለቲካ ስልጣንን ሙዝዝ ብሎ መያዝ እና እንደ መዥገር መጣበቅ ዋናው ተግባሩ ሲሆን ገዥው አካል የህዝብን ገንዘብ በመዝረፍ እና ለብዙሀኑ ህዝብ ህልውና የቆሙትን መሰረታዊ አገልግሎቶች ውሱን ሀብቶች በመቀራመት ግላዊ ሀብትን ለማጋባስ ነው፡፡

የአቶ መለስ የማፊያ (የወሮ በላ) አገዛዝ በሰነድ ብቻ ተመዝግቦ የሚያዝ ሳይሆን በቀድሞው የመከላከያ የትግል ጓደኛቸው ጭምር የአይን ምስክርነት የተሰጠበት ጉዳይ ነው፡፡ ገና ከጫካ ትግል ሲጀምሩ አቶ መለስ እና የትግል ጓዶቻቸው የሌቦች አስተዳደራዊ ስርዓት ነበር የዘረጉት፡፡ እ.ኤ.አ በ1980ዎቹ የመጀመሪያ ዓመታት ለረሀብ ሰለባ ለወደቀው የትግራይ ህዝብ እርዳታ ተብሎ ከእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የተላከውን ከ10 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚሆን ገንዘብ ከተሰጠበት ዓላማ ውጭ አማጺው ቡድን ለጦር መሳሪያ መግዣ እና እራሳቸውን ማበልጸጊያ አድርገውታል፡፡ በቅርብ እየወጡ ያሉ ዘገባዎች እንደሚያመላክቱት ከግማሽ በላይ የሚሆነው የአገሪቱ ኢኮኖሚ በአቶ መለስ ባለስልጣኖች፣ ደጋፊዎች፣ ሎሌዎች፣ ጓደኞች፣ የስራ ባልደረቦች እና ሌሎች ቁጥጥር ስር ተቀፍድዶ ይገኛል፡፡ ሙስናን በሚመለከት የዓለም ባንክ “ሙስናን በኢትዮጵያ መመርመር” በሚል ርዕስ የተወሰኑ አገሮችን ባናሙናነት ወስዶ በማጥናት ባወጣው ባለ500 ገጽ የግኝት ዘገባ መሰረት ሙስና እና የህዝብን ሀብት መዝረፍ በኢትዮጵያ ዋና መገለጫ ሆኗል በማለት ደምድሟል፡፡ ዘራፊነት አና ሙስና የአቶ መለስ የመጨረሻው ውርሳቸው ነው፡፡

አጼ ምኒልክን መጥላት ይወዳሉ፣

ጥላቻ የነብሳችን የመጨረሻው የበሽታ ምልክት ነው፡፡ ጥላቻ ኢምክንያታዊ ነው ወይም አመክንዮ የለውም፡፡ በጥላቻ ላይ የተጻፉ በርካታ ሳይንሳዊ ጽሁፎች እንደሚያመለክቱት በጥላቻ የተመረዙት ምንጊዜም ይጠላሉ ምክንያቱም ይፈራሉ፣ ደህንነት አይሰማቸውም፣ ምቀኞች ናቸው፣ ወይም ደግሞ እራሳቸውን ይጠላሉ ምክንያቱም የጥላቻቸው መነሻ እና መድረሻ እነዚሁ በጥላቻ የተሞሉት ግብዞች ናቸውና፡፡ ከሁሉም በላይ በጥላቻ የተሞሉት ወገኖች እራሳቸውን ይጠላሉ ምክንያቱም ብቁነት የጎደላቸው፣ ኃይልየለሽነት፣ ተስፋቢስነት፣ እና የእረዳትየለሽነት ስሜት የተጠናወታቸው ነው፡፡
ማንዴላ እንዲህ ብለው ነበር፣ “ሰው በቆዳው ቀለም፣ ወይም ደግሞ በማንነቱ፣ ወይም በኃይማኖቱ ምክንያት ብቻ ማንም ማንንም ሊጠላ አልተወለደም፡፡ ሰዎች መጥላትን መማር አለባቸው፣“ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያሉትን የገዥው አካል ኃላፊዎች ሁኔታ በማስብበት ጊዜ በማንዴላ ፍልስፍናዊ ግምገማ ላይ አምነት ማጣት ይቃጣኛል፡፡ ማንዴላ እንዲህ በማለትም አክለዋል፣ “መጥላትን የሚማሩ ከሆነ ፍቅርን ሊማሩም ይችላሉ፣ ምክንያቱም ፍቅር ከተቃራኒው የበለጠ በሰው ልጅ ልብ ውስጥ የመስረጽ ተፈጥሯዊ ባህሪ አለውና፡፡“ ተቃራኒውን በተጨባጭ የሚያመላክቱ በርካታ መረጃዎች ቢኖሩም የማንዴላ መርሆዎች በስልጣን ላይ ባሉት ባለስልጣኖች ሁሉ ሊተገበሩ እንደሚችሉ ጽኑ እምነት አለኝ፡፡

በመርህ እና በተግባርም እንደሚታየው በጋንዲ መርሆዎች መሰረት ለመኖር ጥረት ማድረግ አለብን፣ “ኃጢያተኛውን ሳይሆን ኃጢያቱን እንጥላ፣“ በጥላቻ የተመረዙትን የምንጠላ ከሆነ የእነርሱ የመስታወት ነጸብራቅ እንሆናለን፣ እራሳችንም የምንጠላቸውን እንሆናለን፣ እንደ ሰው ስብዕና አቶ መለስን እና መሰሎቻቸውን የምንጠላ ከሆነ እነርሱኑ ሆን ማለት ነው፡፡ የምንጠላ ከሆነ ምግባራቸውን እንጅ እንደ ሰው እራሳቸውን መሆን የለበትም፡፡

ጥላቻ ጠንካራ ኃይል ነው፡፡ በናዚዝስቶች የተሰራጨው ጥላቻ አገሮችን በጠቅላላ እንዲጠፉ አድርጓል፡፡ በሩዋንዳ የተከሰተው ጥላቻ የሚሊዮኖችን ሩዋንዳውያን ህይወት ቀጥፏል፡፡ በዳርፉር የተቆሰቆሰው ጥላቻ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሱዳን ዜጎችን ህይወት አጥፍቷል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በተከሰተው የኃይማኖት ጥላቻ በናይጄሪያ እና በመካከለኛው አፍሪካ ሬፑብሊክ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በመሞት ላይ ይገኛሉ፡፡ በምንም ዓይነት መንገድ ወደ ጥላቻ መግባት የለብንም፡፡

በዓለም ላይ ሁለት ዓይነት ህዝቦች እንዳሉ አምናለሁ፡፡ “ጎረቤትህን እንደ እራስህ ውደድ“ የሚለውን ወርቃማ ህግ የሚከተሉ ህዝቦች አሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ “የመዳብ ህግ” እያልኩ በምጠራው “ጎረቤትህን እንደ እራስህ ጥላ“ እያሉ የሚኖሩ ህዝቦች አሉ፡፡ በጥላቻ የተሞሉ ሰዎች የእራሳቸውን እረዳትየለሽነት፣ የደህንነት እጦት ስሜት፣ የጥፋተኝነት ስሜት እና በጥላቻቸው መሳሪያነት ድርጊቶችን በመለወጥ አሸናፊነትን የሚጎናጸፉ ይመስላቸዋል፡፡ ሌሎችን በመጥላት የራሳቸውን የበታችነት ስሜት እና የእራስን ዋጋ ዝቅ አድርጎ የማየት ችግራቸውን በማስወገድ እራሳቸውን ከፍ ያደረጉ ይመስላቸዋል፡፡ አጼ ምኒልክን የሚጠሉ ሰዎች በእርግጥ አይጠሏቸውም፣ እራሳቸውን የሚጠሉ እና ምኒልክን ለመሆን የሚያስቡ ምኒልክ የሚያደርጓቸውን ነገሮች ሁሉ ተምሳሌት ለማድረግ የሚጥሩ ናቸው፡፡

በአሁኑ ጌዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ላሉት ሁሉ አዝንላቸዋለሁ፡፡ በእርግጥ በጣም አዝንላቸዋለሁ፡፡ እነዚህ በጥላቻ የተሞሉት ወገኖች የኢትዮጵያን ታላላቅ መሪዎች እና የኢትዮጵያን ታሪክ ጥላሸት በመቀባት በቅርቡ በህይወት የተለዩትን መሪያቸውን እና የሁለት አስርት ዓመታት ኃጢያታቸውን በማስሰረይ ብጹ የሚያደርጓቸው ይመስላቸዋል፡፡ የአጼ ምኒልክን እና የቀዳማዊ ኃይለስላሴን በጎ ተግባራት ጥላሸት በመቀባት የአቶ መለስን ስብዕና የሚገነቡ ይመስላቸዋል፡፡ የአጼ ምኒልክን ሐውልት ከህዝባዊ ቦታዎች በማራቅ እና የአቶ መለስን እርካሽ ወረቀት ፎቶግራፎች በየመንገዶች ላይ በመለጠፍ አቶ መለስን ወደ መልዓክነት ያቀረቧቸው ይመስላቸዋል፡፡ አቶ መለስ የአጼ ኃይለስላሴ ሀውልት ከንክሩማህ ቀጥሎ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ ውስጥ እንዳይቆም ሽንጣቸውን ገትረው ተከራክረዋል፡፡ ሆኖም ግን ንክሩማህ እራሳቸው የአጼ ኃይለስላሴ ያልተጠቆጠበ ጥረት ባይኖር ኖሮ የአፍሪካ ድርጅት እውን መሆን አይችልም ነበር በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያሉት ባለስልጣኖች የጥላቻቸው ባህሪ እና አተገባበር ነጻብራቅ ረዘም ያለ ጊዜ የቆየ ቢሆንም ለዚህ ምክንያታዊ መግለጫ አላገኘሁለትም፡፡ ብዙ ሰዎች በፍርሀት እና በጭንቀት ላይ ያሉ ሰለ ወደፊት ምንይመጣል አያሉ ነው ምክንያቱም በቀጣይነት የሚከሰተው ሁኔታ የማይታወቅ እና ለመተንበይም አስቸጋሪ የሆነበት ሁኔታ ሰለሆነ ነው፡፡ ያለፈውን ጊዜ፣ የጥንት 19ኛውን ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ የሚፈሩትን ሰዎች በትክክል ለመረዳት አልችልም፡፡ በሞያዬ ካለኝ ልምድ አንጻር ያለፈውን ጊዜ የሚፈሩ እና የሚሸበሩ ወንጀለኞ ይሄዉም በፊት በፈፀሙት ወንጀል የሚያዙ ሰለሚመስላቸውና ሰለሚፈሩ ነው:: በስልጣን ላይ ያሉ አምባገነኖች ስልጣናቸውን ከህግ አግባብ ውጭ በመጠቀም የሰላማዊ ዜጎችን መብት የጣሱ እና የደፈጠጡበትን ወንጀል ለመደበቅ ሲሉ ጥላቻን በማራመድ እና ከፋፍሎ መግዛትን አጀንዳቸው አድርገው ይይዙታል ከሚል መደምደሚያ ላይ ደርሻለሁ፡፡ በኢትዮጵያውያን ልዩ ልዩ ጎሳዎች ላይ ጥልቅ ጥላቻና እና ፍርሀትን በመፍጠር ለፈጸሟቸው እኩይ ተግባራት ተጠያቂ እንዳይሆኑ እና ኃላፊነትን እንዳይወስዱ የጥላቻ መንፈስን እንደ መርህ በመያዝ ያራምዳሉ፡፡ በህዝቦች መካከል ጥላቻን በመዝራትም በኢኮኖሚያዊ ችግሮች ምክንያት ተወጥረው ያሉትን ዜጎች ሀሳቦች ለማስቀየሻ ይጠቀሙበታል፡፡

በጥላቻ የተሞላን ሰው እንደ እራስህ ውደድ፣

ወርቃማው ህግ እንዲህ ይላል፣ “ጎረቤትህን እንደ እራስህ ውደድ፡፡“ እኔ ደግሞ እንዲህ እላለሁ፣ “የሚጠላህን እንደ እራስህ ውድ፡፡“ ከመጥላት ይልቅ መውድደ የተሻለ ነገር ነው፡፡ ጥላቻ ወርዋሪውን ተመልሶ እንደሚጎዳ ቦንብ ነው፡፡ መጀመሪያ ከሚወረውረው ሰው እጅ ይወጣል ተመልሶ ግን በጥላቻ የተሞላውን ሰው እራሱን ይጎዳዋል፡፡ የማንዴላን አባባል በመዋስ፣ ጥላቻ የነብስ መርዝ ነው፡፡ በጥላቻ የተሞሉት በሚጠሉበት ጊዜ መርዝን ይጠጣሉ እናም የሚጠሏቸው እንዲሞቱ ይጠብቃሉ፡፡ በስልጣን ላይ ያሉ ሁሉ ጥላቻን ማራመድ እንዳለባቸው ልዩ ምክር የሚሰጥ ለየት ያለ የፍልስፍና ዓይነትም አለ፡፡ ጥላቻ ሁልጊዜ የተጠላውን ሰው የተወደደ እና የተከበረ ስብዕና ያለው እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ተቆናጥጠው ያሉ ወገኖች በዱሮዋ ደቡብ አፍሪካ ከነበሩት የአፓርታይድ መሰል የመንፈስ ጓዶቻቸው ትምህርቶችን ሊማሩ ይገባል፡፡ የአፓርታይድ ጌቶች የማንዴላን ስብዕና፣ አመራር እና ክብር ለበርካታ አስርት ዓመታት ለማዋረድ ፈለጉ፡፡ ማንዴላ አሸባሪ እና ኮሙኒስት ናቸው በማለት ማንኛውንም ዓይነት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ከፈቱባቸው፡፡ ይንንም ምክንያት በማድረግ ማንዴላ በእስር ቤት በቆዩባቸው ጊዚያት ሁሉ ምንም ዓይነት የፎቶግራፍ ምስላቸው እንዳይወጣ አደረጉ፡፡ ሆኖም ግን ያልታሰቡ አጋጣሚዎች ተከሰቱ፡፡ በሂደት ጊዜ እያለፈ እና የጸረ አፓርታይድ ንቅናቄው እየተጠናከረ ሲሄድ ማንዴላን አሳንሶ የማየት አባዚያቸው የማንዴላን የመላዕክነት ደረጃ ከፍ እያደረገ ወደ ዓለም አቀፋዊ ተምሳሌነት እንዲሸጋገሩ እገዛ አደረገላቸው፡፡ ከዚህ ሊወሰድ የሚችለው ታላቅ ቁምነገር የአጼ ምኒልክን እና የአጼ ኃይለስላሴን ስብዕና ዝቅ ለማድረግ ጥረት ባደረጉ ቁጥር እነዚህ መሪዎች በኢትዮጵያ የወጣቶች ትውልድ የአስተሳሰብ አድማስ ዘንድ የበለጠ ክብር እና ሞገስን እየተቀዳጁ ታዋቂ እየሆኑ ይሄዳሉ፡፡ በእነዚህ መሪዎች ላይ የማያቋርጥ እና ዘለቄታዊ ያለው የማዋረድ ዘመቻ ባደረጉ ቁጥር የቀድሞው ትውልድ ጉዳዩን የበለጠ እንዲገመግመው እና አቋሙን እንዲያጠናክር ያደርገዋል፡፡

ፍቅር ከጥላቻ በላይ ዘልቆ መሄድን ይጠይቃል፡፡ ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ እና ማንዴላ በሰዎች እና በህብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ ፍቅር ያለውን የማይበገር የአሸናፊነት ኃይል፣ እንዲሁም ፍቅር በዘር፣ በጎሳ እና በኃይማኖት የተዘራን የጥላቻ ካንሰር የመፈወስ ችሎታ እንዳለው በግልጽ አስተምረውናል፡፡ ማንዴላ ለመጥላት እና በቀልን ለመፈጸም ምክንያት አላቸው፡፡ ለ27 ዓመታት የማንዴላ ስም የእስረኛ ቁጥር 46664 ነበር፡፡ እ.ኤ.አ በፌብሯሪ 1990 ጧት ከእስር ቤት ተለቅቀው ከእስር ቤቱ በር ሲወጡ ከሚሊዮን ዶላር ዋጋ በላይ የሚያወጣውን ፈገግታቸውን አሳይተዋል፡፡ ለ27 ዓመታት ከቤተሰቦቻቸው ነጥለው በእስር ቤት ውስጥ ባማቀቋቸው የአፓርታይድ ጌቶች ላይ ምንም ዓይነት የጥላቻ ስሜት አላሳዩም፡፡ ማንዴላ ታላቅ ትምህርት አስተምረውን አልፈዋል፣ እንዲህ በማለት፣ “እየተራመድኩ ወደ በሩ በምቃረብበት ጊዜ ይህ ሁኔታ ወደ ነጻነት እየመራኝ እንደሆነ አስብ ነበር፡፡ የበቀልተኝነት ስሜቴን እና ጥላቻዬን እዚያው እስር ቤት ጥዬው ካልወጣሁ እዚያው እስር ቤት እንዳለሁ እቆጥረዋለሁ፡፡“ በማለት የጥላቻን መጥፎነት በግልጽ ተናግረዋል፡፡ ማንዴላ ፍጹም የጥላቻ እስረኛ አልነበሩም፡፡ እስረኛው የአፓርታይድ ጥላቻ ነበር፣ እናም አስረኞቹ የአፓርታይድ አለቆች እና ጌቶች ነበሩ፡፡ ማንዴላ ከእስር ቤት በመውጣት በጥላቻ ሰንሰለት ከአፓርታይድ ግንብ ጋር የታሰሩትን እውነተኞቹን የአፓርታይድ እስረኞች ከጥላቻ፣ ከፍርሀት፣ እና ከበቀልተኝነት ነጻ ለማውጣት ተንቀሳቅሰዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያሉት ገዥዎች በጥላቻቸው የሚቀጥሉ ከሆነ በደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ በስልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ የደረሰው ዕጣ ፈንታ የሚደርስባቸው መሆኑን መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡ በአፓርታይድ የአገዛዝ ዘመን ጊዜ “ነጻዎቹ” ነጮች እውነተኛው የማይቀረው የብዙሀን አገዛዝ በሚመጣበት ጊዜ ለብዙ ጊዜ በጭቆና ቀንበር አስረው ሲያማቅቋቸው የነበሩት ጥቁር አፍሪካውያኖች ምን ሊያደርጓቸው እንደሚችሉ ሌት እና ቀን ያሰላስሉ ነበር፡፡ በጥቁር አፍሪካውያን ላይ የነበራቸው ጥላቻ እንቅልፍየለሽ ሌሊቶችን ብቻ እንዲያሳልፉ አላደረጓቸውም፣ ሆኖም ግን ልቦቻቸው፣ አዕምሯቸው እና ነብሳቸው እንዲሁም ስብዕናዎቻቸውም ጭምር እንዲሰበሩ አደረጋቸው እንጅ፡፡ ሙት መንፈሶች አደረጓቸው፣ ነጻ ሆነው ባሏቸው ኃብቶቻቸው ለመደሰት ባለመቻል የቁም ሙት አደረጓቸው፣ እንዲሁም በኤሌክትሪክ እና በእስር ቤት የሽቦ አጥር ታጥረው የእራሳቸው ጎረቤቶች የእስር ቤት በሮች ሆኑባቸው፡፡ በእርግጥ በጦር ካምፕ የሚኖሩ ህዝቦች ሆኑ፡፡
ምንጊዜም የተሻለ መንገድ አለ፡፡ የጥላቻ ትችት ከማቅረባችን በፊት እውነተኛውን ነገር ለማወቅ የበለጠ ጽናት ሊኖረን ይገባል፡፡ ስለዳግማዊ አጼ ምኒልክ፣ ስለ አጼ ኃይለስላሴ፣ ስለ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም እና ስለ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እውነኛውን ነገር ማቅረብ ይኖርብናል፡፡ እነርሱን መጥላት ሳይሆን ከስህተቶቻቸው እንማር፣ እኛ በህይወት ያለነው የእነርሱን ስህተት መድገም የለብንም፡፡ ጥላሸት በመቀባት ላይ ላለመሰማራት ከእነርሱ ስህተት እንማር፣ ነገር ግን የእርቅን መንገድ በመፈለግ የእነርሱን ስህተቶች እናርም፡፡ ከኢትዮጵያ ወጣቱ ትውልድ ጋር ህብረት በመፍጠር ማንም ወንድ ወይም ሴት በማንነቱ/ቷ፣ በዘሩ/ሯ ሳይሆን ሰው በመሆኑ/ኗ፣ አፍሪካዊ/ት እና ኢትዮጵያዊ/ት በመሆናቸው ብቻ በመመልከት አዲሲቷን ፍቅር የነገሰባት ኢትዮጵያ ለመገንባት እንነሳ፡፡ ማንም ወንድ ወይም ሴት ባለው/ላት ስልጣን በመመካት ባልታጠቁ ዜጎች እና በሰላማዊ ሰዎች ላይ የጦር እልቂት ሊያዝዝ/ልታዝዝ የማይችሉበት እና ይህ ዓይነቱ አስተሳሰብም ሊወገድ የሚችልበት ነጻ ህሊናን በመፍጠር አዲሲቷን ፍቅር የነገሰባት ኢትዮጵያ ለመገንባት እንነሳ፡፡ በእያንዳንዱ/ዷ ግለሰብ የጎሳ፣ የእምነት ወይም የቋንቋ ልዩነት ሳንፈጥር በአንድነት በመሆን የእያንዳንዱ/ዷ ዜጋ መብት እና ክብር የሚጠበቅበትን ህብረተሰብ ለመፍጠር እንነሳ፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ነው የወደፊቱን ብሩህ ዘመን ለመፍጠር የምንችለው፡፡ ለብዙ ጊዜ በመቆየት በጊዜ ደመና ተሸፍኖ የደበዘዘውን ነገር ቆፍሮ በማውጣት እና ጥላሸት በመቀባት አይደለም ፍቅር የነገሰበትን የወደፊቱን ትውልድ መገንባት የምንችለው፡፡

በጥላቻ ንግግር አንዘን ወይም ደግሞ አንቆጣ፡፡ ምንም ዓይነት እርባና የለውም፡፡ ይልቁንም ጥላሸት የመቀባት ዘመቻውን በሰከነ መልክ እናጋልጥ፡፡ መላዕክ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ስህተት እና ውሸት መሆኑን እና የኢትዮጵያን ታሪክ ጥላሸት ለመቀበት እና ለመበረዝ የሚደረገውን መዋተት እናጋልጥ፡፡ ከጥላቻ አራማጆች ጋር በማበር እራሳችንን ወደ ጭቃ እና የሚያጣብቅ ቆሻሻ ውስጥ አንጣል፡፡ እንዲህ የሚሉትን የጆርጅ በርናርድ ሻውን ምክሮችን በፍጹም መርሳት የለብንም፣ “ከብዙ ጊዜ በፊት ከአሳማ ጋር ማጥ ዉስጥ ላለመታገል ትምህርት አግኝቻለሁ፣ ለመታገል ከሞከርክ ቆሻሻ ትሆናለህ፣ አሳማው ግን ማጡን የነብሱን ያህል ይወደዋል፡፡“ ጥላቻን ሙያ አርገው ከሚኖሩ ሰዎች ጋር የጥላቻ ቃላትን መለዋወጥ ከአሳማ ጋር በጭቃ ማጥ ውስጥ የነጻ ትግል ውድድርን እንደማድረግ ይቆጠራል፡፡
ጥላቻን ወደ ፍቅር መለወጥ
በጥላቻ መንፈስ የተሞሉት ወገኖች ይጥሉ እና ይዋሹ፡፡ ስለዚያ ጉዳይ የምናደርገው አንዳች ነገር የለም፡፡ በእራሳችን የሀይል ንፍቀ ክበብ ውስጥ ያለን ልዩ ችሎታ እራሳችንን ከጥላቻ ወደ ፍቅር ከመቀየር ላይ ነው፡፡ በእርግጥም አሉታዊ ኃይሎችን ወደ አዎንታዊ ኃይሎች የመቀየር ችሎታ አለን፡፡ ከጥላቻ ወደ ፍቅር ለመቀየር እንችላለን፣ ይህን የምናደርገው ግን ነገሩ ቀላል ስለሆነ አይደለም ይልቁንም የበለጠ ከባድ ስለሆነ እንጅ፡፡ ፍቅር በግለሰብ ደረጃም ይሁን፣ በሌሎችም ይሁን፣ በማህበረሰቡ ወይም በአጠቃላይ በህዝቡ ላይ ይሁን ለተግባራዊነቱ ታላቅ ስራ መስራትን ይጠይቃል፡፡
ከማህተመ ጋንዲ እና “እውነተኛው ኃይል”/Satyagraha ከሚሉት አቀራረባቸው እስቲ ትምህርት እንቅሰም፡፡ ጋንዲ እንዲህ በማለት ገለጻ አድርገዋል፣ “እውነት/satya ፍቅርን በማጎናጸፍ የመንፈስ ጽናትን ይወልዳል፣ እናም ከኃይል ጋር ተመሳሳይ በመሆን ያገለግላል፡፡“ ዓላማው በጥላቻ የተሞላው/ችው እንዳያስገድድ/እንዳታስገድድ በማድረግ ሀሳባቸውን ለማስለውጥ ነው፡፡ በተግባራዊነት ሁኔታው ስንመለከተው ዓላማው በጥላቻ የተሞላውን/ችውን ጥላቻ ማራመድ የእራሱን/ሷን ልብ፣ አዕምሮ እና ነብሳቸውን የሚጎዳቸው መሆኑን በማሳመን እንዲቀየሩ ለማድረግ ነው፡፡ ከማንኛውም ጉዳትን ከሚያመጡ ነገሮች ሁሉ የሚጠብቁን እራስን፣ ማህበረሰቡን እና አገርን መውደድ ነው፡፡ በጥላቻ ከተሞሉት ወገኖች ፍቅር የተሞሉ ወገኖችን ለማፍራት እውነተኛውን ኃይል/Satyagraha በተግባር እናውል፡፡

ከዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ የምንማራቸው በርካታ ቁምነገሮች አሉ፣ እንዲህም በማለት ያስተምሩናል፣ “ጨለማን ጨለማ አያስወግደውም፣ ብርሃን ብቻ ነው ያንን ማድረግ የሚችለው፡፡ ጥላቻን ጥላቻ ሊያስወግደው አይችልም፣ ፍቅር ብቻ ነው ያንን ማድረግ የሚችል፡፡“ ብለዋል፡፡ እንዲህ በማለትም አስተምረዋል፣ “ይቅርታ የማድረግ ችሎታችንን ማሳደግና ማጠናከር ይኖርብናል፡፡ ይቅርታ የማያደርግ/የማታደርግ ሰው ለማፍቀር ኃይል የለውም/የላትም፡፡ በመጥፎነታችንም ላይ ጥሩ ነገሮችም አሉ፡፡ በመጥፎ ነገሮቻችን ላይም ጥሩ ነገሮች አሉ፡፡ ይህንን ሁኔታ ባወቅን ጊዜ ጠላቶቻችንን ከመጥላት በመጠኑም ቢሆን እንታቀባለን፡፡“ ይቅርታ አድራጊነት እና እርቅ ብቸኞች የጥላቻ ፈውስ እና መድኃኒቶች ናቸው፡፡

ከዘመናችን ታላቅ ቀልድ አዋቂ ከቻርለስ ቻፕሊን እንኳ ትምህርት መቅሰም ይኖርብናል፡፡ እንዲህም ይለናል፣ “የሰው ልጅ ጥላቻ ያልፋል፣ እና አምባገነኖችም ይሞታሉ፣ እናም ከህዝቦች የነጠቁት ስልጣን ተመልሶ በህዝቡ እጅ ይገባል፡፡ ስለሆነም የሰው ልጅ ሟች እስከሆነ ድረስ ነጻነት ከናካቴው ሊጠፋ አይችልም፡፡“ ነጻነት በጥላቻ ከተሞሉት የሰው ዘሮች ሁሉ የበለጠ እድሜ አለው፡፡ በጎሳ ማንነት መፈረጅን እርግፍ አድርገን እንተው እና ሰው በመሆናችን ብቻ በኢትዮጵያዊነታችን እና በአፍሪካዊነታችን እንኩራ፡፡

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ላሉ የማስተላለፈው መልዕክት፣

በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ሆነው ጥላቻን ለሚያራግቡት አጭር መልዕክት አለኝ፡፡ በአሁኑ ጊዜ የምትቆሰቁሱት የዘር እና የጎሳ ጥላቻ ፍላጻ በአንድ ወቅት ተመልሶ እራሳችሁ ላይ ይሰካል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የአጼ ምኒልክን ክብር እና ዝና ለማንቋሸሽ በታለመ ዕኩይ ምግባር ጡት ቆራጭ አረመኔ ነበሩ በማለት በመሳለቅ እና በማፌዝ ላይ ትገኛላችሁ፡፡ በአሁኑ ጊዜ አጼ ምኒልክን እንዲጠሉ የሚሰበክላቸው ሰዎች ነገ ደግሞ አቶ መለስን እንዲጠሉ የማይሰበክበት ምክንያት አይኖርም፡፡ የእናንተ ታላቁ ባለራዕይ መሪ አቶ መለስ በኦጋዴን፣ በጋምቤላ፣ በአዲስ አበባ እና በሌሎችም ቦታዎች በንጹሃን ዜጎች ላይ በፈጸሟቸው የጅምላ እልቂቶች ሳቢያ በድንጋይ እና በእብነበረድ በተቀረጹ ሃውልቶች ላይ ሆነው ሁለተኛው ሮዶልፍ ግራዛኒ በመባል የሚታወሱበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም፡፡ ዛሬ ጓደኞች ብላችሁ የያዛችኋቸው ሰዎች ነገ ቀንደኛ ጠላቶቻችሁ ሆነው ይቀርባሉ፡፡ ዛሬ የእናንተ ጠላቶች አድርጋችሁ ጥላሸት የምትቀቧቸው ሰዎች ነገ ጽዋው ሞልቶ እጣ ፈንታችሁ ደርሶ የዘራችሁትን የምታጭዱበት ጊዜ ሲመጣ የእናንተ ጓደኞች ሆነው ይቀርባሉ፡፡

ዳግማዊ አጼ ምኒልክ መልዓክ ወይም ጭራቅ አልነበሩም፡፡ ሰይጣን ወይም ደግሞ እግዚአብሄርም አልነበሩም፡፡ የተቀሩት የአፍሪካ አገሮች በኃአውሮፓ ኢምፔሪያሊስት ኃይሎች ሲቆራረሱ፣ መጫወቻ ሲሆኑ፣ ሲነሱ ሲጣሉ፣ ሲበጠሱ ሲቀጠሉ፣ ሲሸጡ እና ሲለወጡ እንዲሁም ሲጋዙ በነበረበት ጊዜ አጼ ምኒልክ ደግሞ ኢትዮጵያን ሲያጠናክሩ እና ሲያዘምኑ የነበሩ የተከበሩ አፍሪካዊ ንጉስ ነበሩ፡፡ ዳግማዊ አጼ ምኒሊክ በአንድ መለኪያ ብች ይገምገሙ፣ በእውነት! የታሪክ ሰዎች እውነታውን መናገር አለባቸው፣ እና ሁሉንም እውነታዎች፣ ሌላ ምንም ነገር ሳይሆን ስለምኒልክ ያለውን እውነታ ብቻ፡፡ ለአጼ ምኒልክ 100ኛ ሙት ዓመት መታሰቢያ ሲባል እ.ኤ.አ በ1909 በኒዮርክ ታይምስ ባሮን ዲ ጃርልስበርግ የተባለ የቤልጄም አሳሽ ለዳግማዊ አጼ ምኒልክ ምስክርነት ለጋዜጣው ቃል በመስጠት የተዘገበውን በከፊል ምስከርነት እውነታ መረጃ እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ፡፡ ይህ ታሪካዊ የምስክርነት መረጃ ዳግማዊ አጼ ምኒልክን ከሰሯቸው ስራዎች አንጻር በትክክለኛው የታሪክ ሚዛን ላይ በማስቀመጥ እንዲገመገሙ ያስችላል የሚል ጽኑ እምነት አለ፡፡

ዳግማዊ አጼ ምኒልክ የዘውድ ስልጣኑን ለመቆናጠጥ ትግል ማድረግ ከጀመሩበት ከ20 ዓመታት በኋላ አቢሲኒያን ከከፊል የኋላቀርነት አገዛዝ በማውጣት ወደ አውሮፓውያን የንጉሳዊ ህገመንግስት የአገዛዝ ስርዓት ምሳሌነት አሸጋግረዋታል… እራሳቸውን ነጻ እና በእራስ የሚተማመኑ አድርገው የሚቆጥሩት ዘ እምነገደ የይሁዳ አንበሳ ስዩመ እግዚአብሔር የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ የኢጣሊያንን የቅኝ ግዛትነት ፍላጎት አምባ ጋሪማ ላይ ጦርነት ገጥመው በአሸናፊነት እንዳንኮታኮቱት… አጼ ምኒልክ ከአጼ ዮሀንስ ህልፈተ ህይወት በኋላ እ.ኤ.አ ኖቬምበር 4 1889 የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ሆነው ሲሰየሙ የአቢሲኒያን መንግስት ከመሰረቱት የአካባቢያዊ መንግስታት በሙሉ ቅቡልነት አልነበራቸውም፡፡ ከብዙ ድካም እና ትግል በኋላ ነው እነዚህን የአካባቢ ገዥዎች እና ንጉስነታቸውን አንቀበልም ያሉትን አማጺ ገዥዎች በማሳመን እና በኃይል በማንበርከክ በመጨረሻ ስኬታማ ለመሆን የበቁት… ከዚያ በኋላ የአጼ ምኒልክ ዋና ዓላማ የነበረው የአውሮፓን ስልጣኔ ወደ አገራቸው ማስገባት ነበር፡፡ ንጉሱ የፊውዳሉን ህግ በማፈራረስ በእርግጥም በግዛታቸው እስከ አሁንም ድረስ ጨርሶ እንዳልጠፋ እና ባሮችን ነጻ በማውጣት የባሪያ ንግድን በማጥፋት በግዛታቸው በሙሉ ከክፍያ ነጻ የሆነ የትምህርት ስርዓትን ዘርግተዋል፡፡ በዚህም መሰረት እንደማንኛውም የአውሮፓ ሀገር ሁሉ በቀጣዮቹ ትውልዶች ትምህርት በመላ የአቢሲኒያ ግዛት ውስጥ የሚስፋፋ ይሆናል፡፡

ምኒልክ በመላ አፍሪካ በስልጣን ላይ ካሉ መሪዎች ሁሉ ልዩ ባህሪ ያላቸው ናቸው፡፡ እንደ የዲፕሎማሲ ሰው፣ እንደ ገንዘብ ኃላፊ፣ እንደ ወታደር ከሌሎች ወንድማዊ ንጉሶች የቅርበ መረጃዎችን በመውሰድ በእራሳቸው አካሄድ እንደሚመስላቸው የሚተረጉሙ ንጉስ ናቸው፡፡ እንደ ወታደር እና እንደ የዲፕሎማሲ ሰው የኢጣሊያኖችን በአቢሲኒያ መሸነፍ ለንጉሱ እንደ መልካም አጋጣሚ ምን ያህል ጠቃሚ የሆኑ ንጉስ መሆናቸውን አሳይተዋል፡፡ በቅርብ ዓመታት ደግሞ የገንዘብ ብልህ ጥንቁቅ አያያዝ ምኒልክን ልዩ ያደርጋቸዋል፡፡ ስለገንዘብ እንደ ወጣትም፣ የዙፋን ስልጣናቸውን ከመያዛቸው እና በዙፋኑ ላይ ከተቀመጡም በኋላ በፓሪስ የስቶክ ገበያ ትንበያን/Paris Bourse ላይ ተሳትፎ ማድረጋቸው መልካም ተፈጥሯዊ ችሎታ ያላቸው መሆኑን ያመላክታል፡፡ እነዚህ ጠቃሚ ትንበያዎች የነበሩ ሲሆን ምኒልክ የዙፋን ስልጣኑን ከያዙ በኋላ ለመቋረጥ ችለዋል… የገንዘብ አሰራር ስርዓታቸውን በማስፋት እስከ ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ድረስ በማስፋት በአሜሪካ የባቡር ሀዲድ ካምፓኒዎች ላይ ትልቅ የድርሻ ባለቤት ለመሆን በቅተዋል፡፡ ከአሜሪካ የሴኪዩሪቲ ሰርቲፊኬቶች እና ከፈረንሳይ እና ከቤልጄም ባለሀብቶች ጋር ከ25 ሚሊዮን ዶላር ያላነሰ መዋዕለ ንዋይ በስራ ላይ እንዲውል አድርገው ነበር፡፡
በጣም የሚያስገርመው የአቢሲኒያው ደብዛዛ ንጉስ በሁሉም ነገሮች ላይ ያላቸው ሁለገብ እውቀት ነው፡፡ በጣም ምጡቅ የቋንቋ ችሎታ የነበራቸው ሲሆኑ ፈረንሳይኛ፣ እንግሊዝኛ እና ጣሊያንኛ ቋንቋዎችን አቀላጥፈው መናገር ይችላሉ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ለመንግስታዊ ስራቸው ሙሉ ጊዜ ሰጥተው የሚሰሩ ሲሆን በአውሮፓ የሚዘጋጁ ጽሁፎችንም የመከታተል ዕድል ስላላቸው እና በትኩረት ስለሚከታተሉ አዲስ መጽሀፍ በወጣ ቁጥር ስለደራሲው ሲጠየቅ አዲስ አይሆኑም፡፡ ባዲሳባ ቤተመንግስት በሰዎቻቸው በሚታወቁበት መጽሀፍትን በማሰባሰብ ስራቸው እውቅና እንዲሰጣቸው ሲባል በተዘጋጀው ስብሰባ ላይ በተገኙበት ዕለት በቤተ መጻህፍታቸው ከ20 ሺህ ያላነሱ ጥራዞች መገኘታቸው ልዩ ኩራት እንዲሰማቸው አድርጓል፡፡ የምኒልክ መጻህፍትን የማሰባሰብ የትርፍ ጊዜ ስራ በጥንት የአፍሪካ እና የኢስያ ስልጣኔዎች ዘመንም የሚደረግ ነበር፡፡

በአጼ ምኒልክ ላይ የጥላቻ ዘመቻ ከሚያደርጉት ወገኖች ጋር የማቀርበው መደራደርያ ፣

በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ላይ የጥላቻ ዘመቻ ስለማሰራጨት ጉዳይ የማቀርበው መደራደርያ አለኝ ፡
በአጼ ምኒልክ ስብዕና ላይ የምታደርጓቸውን ውሸቶችና ቅጥፈቶች የምታቆሙ ከሆነ እኔም ስለአቶ መለስ የምናገራቸውን እውነቶችመናገር አቆማለሁ!
ጥር 7 ቀን 2006 ዓ.ም

አንድነት በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ማካለል ዙሪያ ሕዝባዊ ውይይት ሊያደርግ ነው

$
0
0

ከያሬድ አማረ/ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ

UDJአንድነት ፓርቲ ጥር 18/2006ዓ.ም በኢትዮ ሱዳን ድንበር ማካለል ዙሪያ ከህዝብ ጋር ውይይት እንደሚያካሂድ አስታወቀ።

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በኢትዮ ሱዳን የድንበር ማካለል በሚል በሁለቱ መንግስታት ብቻ በሚስጥር በተያዘው መርሀ ግብር ዙሪያ ከህዝብ ጋር ውይይት እንደሚያደርግ ተገልጧል፡፡

ፓርቲው በመጪው ጥር 18ቀን 2006ዓ.ም የሚያካሂደው ህዝባዊ ውይይት በኢትዮጵያ በመንግስትና በሱዳን መንግስት መካከል ይፋ ባልሆነው የድንበር ማካለሉ ሂደት ግልፅነት የጎደለው የድንበር ማካለል በሚል ሽፋን ሊደረግ የታሰበና በአካቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ለሰቀቀን የዳረገ ከመሆኑም ባሻገር በጉዳዩ አሳሳቢነት ዙሪያ መወያየት አስፈላጊ በመሆኑ ፓርቲው ከህዝብ ጋር ተወያይቶ ግልፅ አቋሙን የሚያሰቀምጥበት በመሆኑ የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ሁሉ በውይይቱ ላይ በመገኘት ሃሳቡን እንዲገልፅ አንድነት ጥሪውን አቅርቧል፡፡

በሌላ ዜና አንድነት ፓርቲ ለአማራ ክልል እና ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የኢትዮ ሱዳን ድንበር ማካለል ጉዳይ በአጭር ግዜ ውስጥ ለህዝብ ግልፅ እንዲሆን በደብዳቤ አሳሰበ።

አንድነት ለአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደርና ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በኢትዮ ሱዳን የድንበር ማካለል ዙሪያ ግልፅ የሆነ ማብራሪያ በአጭር ግዜ ውስጥ ለህዝብ እንዲሰጥ በደብዳቤ ጠይቋል።

የአንድነት ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ለፍኖተ ነፃነት እንደገለፁት ኢህአዴግ በሉአላዊ ግዛት ማስከበር ጉዳይ የግዴለሽ አመለካከት ያለው በመሆኑ ብሔራዊ ጥቅማችንን ሊጎዳ የሚችል እርምጃ ሲወስድ በመቆየቱና የተለማመድው በመሆኑ አሁንም በተለመደው ግብሩ ለህዝብ ግልፅ ባልሆነ ሁኔታ ሊካሄድ የታቀደው የድንበር ማካለል የኢትዮጵያን ጥቅም ባላስጠበቀ መንገድ ሊፈፀም እንደሚችል ፓርቲው ከፍተኛ ስጋት ስላደረበት ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለና በሚስጥር የያዘው የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳደርም ሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ ስለ ድንበር ማካለሉ አጠቃላይ ዝርዝር ሁኔታ ለህዝቡ በአጭር ግዜ ውስጥ ግልፅ የሆነ ማብራሪያ እንዲሰጥ በደብዳቤ መጠየቃቸውን ገልፀዋል፡፡


የመረጃና የሃሳብ ነፃነትን ለጋራ ጥቅም እናውለው! –ቃልኪዳን ከኖርዌ

$
0
0

kalkidanቃልኪዳን ካሳሁን /ከኖርዌ

ሀገሪቱ እየገነባች ያለው ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የፈጣን ልማት ባለቤት አላደረጋትም። ባለፉት ሺ ዓመታት በኢትዮጵያ ያልነበረ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንድንጀምርና በጋራ እንድናሳድግ እድል አልፈጠረም። ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ከመለያየትና ከፀረ እኩልነት አስተሳሰብ ወጥተው መከባበር፣ መደጋገፍና በልዩነት ውስጥ አንድ ሀገር መገንባት እንዲጀምሩ አላገዘም።

Read full Story in PDF

“የአንድነት ፓርቲ የመጪው ጊዜ ፈተና”–የመልስ መልስ ለአቶ ግርማ ካሳ እና ለመሰሎቻቸው –ከፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)

$
0
0

“የአንድነት ፓርቲ የመጪው ጊዜ ፈተና” በሚል ርዕስ ለጻፍኩት ጽሁፍ ስለሰጡት ምላሽ ከልብ አመሰግናለሁ። ሀሳቦችን በጨዋ መንገድ ማንሸራሸር ለእድገት ይጠቅማልና ሁላችንም ይልመድብን እላለሁ። ስለአንድነት ፓርቲ ተቆርቋሪ ሆነው የሰጡት መልስ ብዙም እንዳላረካኝ ስገልጽልዎ በከፍተኛ አክብሮት ነው። ማንም ጤናኛ ሰው በአገር ውስጥ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ዴሞክራሲያዊ ለውጥ እንዲመጣ ይፈልጋል። አንድነት ፓርቲ በዚህ እምነት የሚያደርገውን ትግልም አደንቃለሁ። ይሁን እንጅ የትግል ፍሬ መለኪያው ሂደት ሳይሆን ውጤት ነውና አንድነት ፓርቲ፣ ኢ/ር ግዛቸው ሊሄዱበት ባሰቡት መንገድ ከተጓዘ፣ ውጤታማ ይሆናል የሚል እምነት የለኝም። እርስዎ በዚህ አስተያየት አልተስማሙም። አለመስማማትዎን ሁለት ቁምነገሮችን በማንሳት ለማሳየት ሞክረዋል፤ እኔም በእነዚህ ነጥቦች ላይ ተመስርቼ የመልስ መልስ አቀርባለሁ።

አንደኛ፤ አንድነት ፓርቲ፣ የአገሪቱ የህግ አካል የሆነውን ፣ የምርጫ ስነምግባር መመሪያው እስካሁን አለመፈረሙ ስህተት ነበር፣ አሁንም ፈርሞ ከኢህአዴግ ጋር መነጋገር አለበት የሚል መከራከሪያ አቅርበዋል። የስነምግባር መመሪያውን ፈርመው ለድርድር ተቀምጠው የነበሩት የቀድሞው የመኢአድ ሊቀመንበር ኢ/ር ሃይሉ ሻውል በመጽሀፋቸው የተናገሩት ሰነዱን መፈረም ያዋጣል አያዋጣም የሚለውን ለማየት ይረዳናልና ልጥቀስ፤-

Hailu Shwel ” ከኢህአዴግ ጋር ያደረግነውን ድርድር በተመለከተ አንዳንዱ ‘ ወደሰለጠነ ፖለቲካ ልንገባ ይሆን?’ ብሎ በደህና ሁኔታ ያየው ወገን ነበር። ሌላው ወገን ግን ‘እንዴት ያሰረውን ሰው ሄዶ እጅ ይጨብጣል’ የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አሰምቷል። የ2002ቱን የምርጫ ስነምግባር ሰነዱን ስንፈርም ተቃውሞ እንደሚኖር ሳናውቅ ቀርተን አይደለም። ፊርማው ብቻውን ለእኛ ደስታን የሚሰጠንም ሆኖ አልነበረም።ሌላኛው አማራጭና አስተሳሰብ ግን ግብዝነትናን የሚያጠናክርና የሰላም ሂደትን የሚገታ ይሆናል የሚል ግምት መያዛችን አንዱ ምክንያታችን ነው። በወቅቱ እኛ ሰነድ መፈረማችን ለህዝብ ምን ፋይዳ አለው የሚለውንም በአግባቡ አይተነዋል። እኛ ያሰብነው ወረቀት ቢሮ ውስጥ ይፈረማል፣ ያልቃል የሚል ነበር። እነሱ ግን አምባሳደሮች ጋብዘው፣ ሚዲያዎችን ጠርተው የተለየ ዝግጅት አደረጉ። ነገሩን ለዓለም ለማሳወቅ መፈለጋቸው ለሁሉም ግልጽ ሆነ። በዚያን ወቅት እኛ የማናውቀው ውጥረት ነበረባቸው የሚል የዘገየ ግምት ተከሰተልኝ ። እኔ እንደሚመስለኝ የአውሮፓ ህብረት ታዛቢዎች የመታዘብ ይሁንታ የሰጡት ያ ስምምነት ስለተፈረመ ይመስላል። መኢአድ ሰነዱን የፈረምንበት ዋናው ምክንያት ግን የ500 ስቃይ ላይ የነበሩ እስረኞችና የቤተሰቦቻቸው ሰቆቃ አሰቃይቶን ነው። እኔን በተመለከተ ኢህአዴግ ወደ እኛ አስገባነው ብሎ ቢያስወራም አልሰመረለትም።”

(ህይወቴና የፖለቲካ እርምጃየ፣ ሃይሉ ሻውል፣ ገጽ139)።

አቶ ግርማ እዚህ ላይ አራት ነጥቦችን ላንሳ። አንደኛው፣ አቶ ሃይሉ እንዳሉት የስነምግባር መመሪያው ለኢህአዴግ አለማቀፍ ተቀባይነትን ለማሰጠት ጠቅሟል። ቢያንስ የምርጫ ታዛቢ እንዲላክ አድርጓል። የታዛቢው የመጨረሻ ሪፖርት ባያምርም። ሁለተኛ አቶ ሃይሉ 500 ሰዎችን ከእስር ለማስፈታት ብለው እንጅ ሙሉ በሙሉ አምነውበት ሰነዱን አለመፈረማቸውን ገልጸዋል። ልብ ይበሉ አቶ ግርማ! ከ80 ሚሊዮን እስረኞች የተፈቱት 500 ዎቹ ብቻ ናቸው። 80 ሚሊዮኑ ህዝብ ከእስር እንዲፈታ ስንት የምርጫ ስነምግባር ፊርማዎችን መፈረም ይኖርብን ይሆን? ሶስተኛ ፣ መኢአድ ፊርማውን መፈረሙ ህዝቡ እንዲከፋፈል አድርጎታል። አንድነትስ ተመሳሳይ ነገር አይሰራም ብለው ያስባሉ? የሚከፋፈለውን ህዝብ አንድ ለማድረግ እርስዎ የህዝብ ግንኙነት ስራ ለመስራት ተዘጋጅተዋል? አይርሱ ፖለቲካ 50 በመቶው ገጽታ ( image) ነው። አራተኛ፣ ኢህአዴግ የፊርማውን ስነስርአት ለራሱ የፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ተጠቅሞበታል። በድብቅ ይፈረማል የተባለውን ፊርማ ለአደባባይ አብቅቶታል። በአንድነት ላይስ እንዲህ እንደማይደረግ ምን ዋስትና አለ? በህዝቡ ላይ የሚፈጥረውን አሉታዊ ስሜትስ እንዴት ነው መቋቋም የሚቻለው?

ኢ/ር ሃይሉ ሻውል አያበቁም፣ ይቀጥላሉ ” በሌላ በኩል ከህዝቡ ወገን ደግሞ ” ሃይሉ ከዳን” የሚልም ነበር። ውጪ አገር ያሉትማ በኢንተርኔት ላይ ፎቶግራፌን እያገላበጡ እኔ ለቀድሞው ጠ/ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊ እጅ እንደምነሳ አስመስለው ሲዘልፉኝ ከርመዋል።… የሰነዱ መፈረም ለ2002 ምርጫ ዝግጅት ለእኛ አባላት ትንሽ ፋታ ሰጥቷል። ገጠር ሲታገሉ የሰነበቱት እሳት ውስጥ ነበሩ፤ ከፊርማው በሁዋላ ለአጭር ቀናት ቢሆንም በመጠኑ ማስፈራራት ጋብ አለ።” ይሄ ፊርማውን በመፈረም የተገኘ ጥሩ ዜና ነው አቶ ግርማ። ግን ይቀጥል ይሆን ? እንመልከተው፦ ” ምርጫው እየተቃረበ ሲመጣ ግን ሁሉም ነገር ተረሳና ኢህአዴግ የተለመደ ጭቆናውን ማስፋፋት ተያያዘው… መኢአድ ከ2002 ምርጫ ጋር ተያይዞ ከኢህአዴግ ጋር የስነምግባር ደንቡን ከፈረመ በሁዋላ በኢህአዴግ በኩል የተገቡ ቃሎች ባለመተግበራቸው ከጋራ መድረኩ ራሱን አግልሏል። ኢህአዴግ ሁሉም ነገር በቁጥጥር ስር እንዲሆን ፈለገ። በመድረኩም እንነጋገር ብለን የምንጠይቀውን አጀንዳ አይቀበሉትም። የሄ ከሆነ የጋራ ስምምነት የምክክር አይደለም ብለን ተውነው። ስንመለከተው ኢህአዴግ ትእዛዝ የሚያስተላልፍበት መድረክ ስለሆነ ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ግንባታ ጸር እንጂ ጠቃሚ አለመሆኑን በገሀድ ታየ። ገዢው ፓርቲ በዚህ በጋራ መድረክ አባልነት የቀጠሩትን ፓርቲዎች ደመወዝ መሰል ድጎማ እየከፈለ በቁጥጥር ይዟቸው ቀጥሎአል።በ2002 የስነምግባር ደንቡን ብንፈርምም የእኛ አባሎች ላይ የሚደርሰው ወከባና እንግልት ከዚያ በሁዋላ እየቀጠለ መጣ…” ይሉና አቶ ሀይሉ ይቀጥላሉ…
አቶ ግርማ ካሳ እንግዲህ አንድነትንም ወደዚህ የአራዊቶች ጉባኤ ( ፋቡላ) በመክተት ፓርቲውን በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር ሊያደርጉት እና ደሞዝ ሊያሰፍሩለት ያስባሉ ማለት ነው። ለአንድነት ፓርቲ ታጋዮች ካለኝ ከበሬታ አንጻር ፓርቲው በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር እንዲሆን አልመኝም። ወርሃዊ ደሞዝ እንዲሰፈርለትም አልሻም።ምክንያቱም እንዲህ አይነቱ አካሄድ ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል የሚገድል ነውና ።

መድረክም አንድነትም ፊርማውን እስከዛሬ ባለመፈረማቸው የረባ ውጤት አላገኙ ይሆናል፤ ነገር ግን ” No to cheating!” በማለታቸው ከመኢአድ የተሻለ ክብር እና ድጋፍ አግኝተው እንደነበር አንዘነጋውም።

andu_udjሁለተኛው መከራከሪያዎ አቶ አንዱዓለምንና ናትናኤልን በተመለከተ የሰጠሁትን አስተያየት ተንተርሶ የቀረበ ነው። እኔ አንድነቶችን ከመከፋፈል ማዳን እንጅ፣ እነሱን የመከፋፈል አላማ የለኝም፣ በፍጹም!። ይሄን ስጽፍም ፓርቲውን ከመከፋፈል ለማዳን እንጅ ለሌላ አላማ አይደለም። ወ/ት ብርቱካን እስር ቤት ከገባች በሁዋላ ፓርቲዋ ( አመራሩ) ረስቷት ነበር። እንዴያውም አንዳንዶች “እንኳን ታሰረች” ሳይሉ ሁሉ አልቀረም። ያን ጊዜ ማን ነበር ለብርቱካን አብዝቶ የጮኸው? ዲያስፖራው እና በተለይ ኢሳት አልነበሩምን? የካናዳው ልጅ ተክሌ ” ብርቱካኔ ብረሳሽ ቀኜ ይርሳሽ” ብሎ ዜማ ያወጣላት አምስተርዳም የኢሳት ስቱዲዮ ውስጥ ሆኖ ነው። በወቅቱ የነበሩ ባልደረቦቼ ብርቱካንን በተመለከተ ብዙ ዝግጅቶችን ይሰሩ ነበር። ምንም እንኳ ኢሳት እዚህ ውስጥ እንዲገባ ባልሻም፣ “የኢሳቱ ባልደረባ” እያሉ ስለጻፉና በተዘዋዋሪም እኔ የጻፍኩትን የኢሳት አቋም አድርገው ለማሳየት ስለሞከሩ ትንሽም ብትሆን እውነቱን ለመናገር ይጠቅማል ብየ ስላሰብኩ ነው ኢሳትን መጥቀሴ። ( በነገራችን ላይ ኢሳት የግል አስተያየቴን እንዳልጽፍ እያደረገኝ ነው፣ በግሌ የምጽፈውን አንባቢዎች ” የኢሳት አቋም አድርገው ይወስዱብኝ ይሆን” እያልኩ በመስጋት፣ መጻፍ እየፈለኩ አልጽፍም፤ ለሀሳብ ነጻነት በሚታገል ድርጅት ውስጥ የምሰራ ሰው፣ በዚሁ ድርጅት መልሼ መታፈኔ ይገርመኛል፤ ያፈነኝ ግን ድርጅቱ ሳይሆን፣ ሰዎች ከድርጅቱ ጋር ያያይዙብኝ ይሆን የሚለው ፍርሀት ነው።)

አንዱዓለምና ናትናኤል የብርቱካን እጣ እንዲገጥማቸው አልሻም። በፓርቲው ሸውራራ አካሄድ ስነልቦናቸው እንዲጎዳም አልፈልግም፤ የስነምግባር ደንቡን መፈረም አንዱዓለምን እና ናትናኤልን ከእስር እንደያማያስፈታ አስረግጬ መናገር እችላለሁ። እነሱን የማያስፈታ ሰነድ ደግሞ ጥንቅር ብሎ ይቅር። አንዱዓለምና ናትናኤል በመረሳታቸው እጅግ ያንገበግበኛል። የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጉና የገንዘብ መዋጮ የመሰብሰቡ ስራ እንኳ ቆሟል። ይሄ አልበቃ ብሎ በደንብ ባልተጠና የፖለቲካ አካሄድ ስነልቦናቸው ሲጎዳ አይቶ በሁዋላ ከመጸጸት አሁን የሚመስለንን መናገሩ ይጠቅማል እንጅ አይጎዳም።
እነ አንዱዓለም ያልመከሩበት ፖሊሲ በምንም ታዕምር ተግባራዊ መሆን የለበትም! አንዱዓለም የታሰረው ሮቢን አይላንድ አይደለም! ማማከር ይችላል። አንዱዓለም ” አይቃወምም ፣ ይስማማል” በሚል የሚቀርበው መከራከሪያ ብዙ መንገድ አይወስድም።

አንዱአያም አራጌ ” ያልተሄደበት መንገድ” በሚለው መጽሀፉ በገጽ 58 ላይ ስለ አምባገነኖች ባህሪ የጠቀሰው ትክክለኛ ነው እላለሁ ” የአለም ታሪክ እንደሚያሳየው አምባገነኖች በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣናቸው ለቀው አያውቁም። እንደውም እነርሱ ስልጣን ከለቀቁ ሀገር እንደሚበታተን፣ ህዝብ እንደሚጨራረሽ የማስፈራሪያ ፕሮፓጋንዳ ይነዛሉ። ፈርተው ያስፈራሉ። ይሄ ባህሪያቸው መሆኑን መረዳትና ያለመዘናጋት መታገል ያስፈልጋል… ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ አሁን ያለውን አገዛዝ ለህዝብ ፈቃድ እንዲገዛ የግድ ማለት ያስፍልጋል።”

እኔ ነገ ስለሚሆነው ነገር ነው የምጽፈው፣ ትክክል መሆንና አለመሆኔን ለማየት ትንሽ ጊዜ መጠበቁ የሚሻል ይመስለኛል። ተሳስቼም ከሆነ ያን ጊዜ ሂሳቤን አወራርዳለሁ። ( በነገራችን ላይ አንድ ጊዜም እንዲሁ ሰማያዊ ፓርቲ በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዱን በመቃወሜና ቀኑን እንዲቀይረው በመጠየቄ ብዙ ትችቶችን አስተናግጃለሁ፤ በሁዋላ ፓርቲው ( የእኔን ምክር ሰምቶ ይሁን አይሁን አላውቅም) ቀኑን ቀየረው፤ ለወረደብኝ ትችት ግን ሂሳቡን ያወራረደልኝ ሰው አልነበረም፤ ሲጽፉብኝ የነበሩ የማውቃቸው ሰዎች ሳይቀር ድምጻቸውን አጠፉ። እኔ ከተሳሳትኩ ሂሳቤን እንደማወራርድ ቃል እገባለሁ፣ ለመመጻደቅ ሳይሆን ለእድገት ይጠቅማል ብየ ስለማምን ነው።)

(ሰበር ዜና) በትግራይ ክልል በአጽቢ ወንበርታ በሕዝብ እና በአስተዳዳሪዎች መካከል ጸብ ተነሳ፤ 37 ጊዜ ጥይት ተተኩሷል

$
0
0

(አብርሃ ደስታ ከመቀሌ)

(አብርሃ ደስታ ከመቀሌ)

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ እንደዘገበው ይህ ዜና እየተዘገበ ባለበት ሰዓት (ሓሙስ 08/05/06 ዓም ከቀኑ 11:30 ጀምሮ) በትግራይ ክልል በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ (ጣብያ ሩባ ፈለግ ቁሸት ሕኔቶ) በህዝብና አስተዳዳሪዎች መካከል (በውኃ አጠቃቀም ምክንያት) በተፈጠረ አለመግባባት ሃይለኛ አምባጓሮ ተፈጥሯል። ፖሊሶች ተኩስ ከፍተዋል። እንደ አብርሃ ዘገባ ከ11:30 እስከ 11:40 ሰዓት ባለግዜ ለሰላሳ ሰባት (37) ግዜ ተተኩሷል።

“ምልሻዎች በተጠቀቅ ይገኛሉ።” ያለው የአብርሃ ዘገባ “የመንግስት የሚድያ ሰዎች ሂደቱ እየቀረፁት ነው። የቆሰለ ውይም የሞተ ሰው ስለሞኖሩ ወይ አለመኖሩ በግርግሩ ምክንያት ለማወቅ አልተቻለም። ተኩሱ እየቀጠለ ነው።” ብሏል።

አብርሃ በፌስቡክ ገጹ ጨምሮም በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ ህዝብና አስተዳዳሪዎች መካከል ባጋጠመ ግጭት ፖሊስ ቢተኩስም ችግሩ ከፖሊስ አቅም በላይ በመሆኑ አሁን አስተዳደሩ የመከላከያ ሰራዊትን እርዳታ ጠርቷል። አሁን የመንግስት ምልሻዎች በአካባቢው እየተሰማሩ ይገኛሉ። በግጭቱ የተሳተፈው ኗሪ ህዝብ ከሺ በላይ ይሆናል። እስካሁን ድረስ የኗሪው ህዝብ ተወካዮች የነበሩ አራት ሰዎች የት እንደገቡ አይታወቅም። ፖሊሶች ህዝቡን ለመበተን ሃይል ቢጠቀሙም ህዝቡ ግን አራቱ ተወካዮቹ ካልተለቀቁ ላለመበተን አድማ መቷል። ህዝብ እየተሰባሰበ ነው። (የተኩስ ድምፅ በስልክ አስደምጠውኛል)።

በዚህ ዜና ዙሪያ ዘ-ሐበሻ ዘርዘር ያለ መረጃ ከደረሳት ለማቅረብ ትሞክራለች።

ዛሬ በትግራይ ትግል አጽቢ ወንበርታ በፖሊስ እና በሕዝብ መካከል ስለተነሳው ግጭት የአብርሃ ደስታ የቀጥታ (Live) ዘገባዎች

$
0
0

የአፅቢ ግጭት

አብርሃ ደስታበአፅቢ ወንበርታ በተከፈተው ግጭት የመንግስት ፖሊሶች ተኩስ መክፈታቸው፣ አርሶአደሮች መደብደባቸው፣ እንዲሁም አራት የኗሪዎቹ ተወካዮች በሃይል አስረው ወዳልታወቀ አከባቢ መውሰዳቸው ታውቋል። ህዝቡም (የአካባቢው ምልሻዎች ሳይቀሩ) አስራ ሁለት ፖሊሶችና አንድ የመንግስት ምልሻ ከበው አግተው ይዟቸው ቆይተዋል። አራቱ የህዝቡ ተወካዮች እስካልተለቀቁ ድረስ ፖሊሶቹ እንደማይለቀቁ የአርሶ አደሮቹ ተወካዮች አሳውቀው ነበር። አሁን በተደረገ ድርድር አራቱ ተወካዮች ይፈታሉ፣ በህዝቡ ታግተው የነበሩ አስራ ሁለት ፖሊሶችም ይለቀቃሉ። ህዝቡ የአራቱ ሰዎች መለቀቅ እየተጠባበቀ ይገኛል። ፖሊሶቹ ተለቀዋል፤ አራቱ ገብሬዎች እስኪፈቱ ድረስ ግን እዛው ይቆያሉ። መከላከያ ሰራዊት ጥሪ ቢቀርብላቸውም እስካሁን ድረስ (እስከ ምሽቱ 1:30) ባካባቢው አልደረሱም።

ድርድሩ አልተሳካም፡ ተኩስ ተከፍቷል ህዝብ እየተደበደበ ነው

ፖሊሶች አራት የኗሪዎቹ ተወካዮች በሃይል ሲወስዱ የአፅቢ ህዝብም አስራ አራት ፖሊሶችና አንድ ምልሻ አግተው ነበር። ህዝቡ ፖሊሶቹ እንዲለቅ አስተዳደሩ ደግሞ አራቱ ተወካዮች እንዲለቅ ድርድር ተጀምሮ ነበር። በድርድሩ መሃል የወረዳው አስተዳደር አዲስ ሃይል በመጥራት (ከሌላ ወረዳና ከክልል አስተዳደር የፀጥታ ሃይሎች በመላክ) ህዝብ በተሰበሰበብት መተኮስ ጀመሩ (ከምሽቱ 2:30-2:56)። ምልሻዎቹና ወታደሮቹ የታገቱትን ፖሊሶች ለማስለቀቅ እስከ ሁለት መቶ (በኗሪዎቹ ግምት መሰረት) የሚደርስ ጥይት በመተኮስ የታገቱት ፖሊሶችን ማስለቀቅ ችለዋል። እስከ ሁለት ሺ የሚጠጋ ህዝብ ተሰብስቦ እየጨኸ ይገኛል። አሁን (ከምሽቱ ሦስት ሰዓት) ብዙ ምልሻዎች የጫኑ ብዙ መኪኖች ወደ አከባቢው እየገቡ ነው። በሌላ አቅጣጫ (በስተ ሰሜን በኩል) ደግሞ ሌሎች ብዙ መኪኖች እየገቡ ነው (ምልሻ ወይ ፖሊስ ወይ ወታደሮች መሆናቸው ግን በትክክል አይታወቁም)። ህዝብ በዱላ መደብደብ ጀምረዋል። ህዝቡ እየጮኸና ፈጣሪው እየለመነ ነው። የህዝቡ ጩኸትና ለቅሶ በስልክ መስማት ችያለሁ። እያናግሩኝ ያሉ ሰዎችም መረጋጋት ተስኗቸዋል። አሁን ከምሽቱ 3:05 ሁነዋል።

ተኩሱ ቆሟል፣ ምልሻዎቹ ለሁለት ተከፍሏል፣ ወታደሮች ገብተዋል

ታግተው የነበሩ የመንግስት ፖሊሶች ሌሎች ፖሊሶችና ምልሻዎች በከፈቱት ተኩስ ተለቀዋል። አሁን ህዝቡና የመንግስት ምልሻዎች በሜትሮች ርቀት ተለያይተው ማዶ ለማዶ ይተያያሉ። የአፅቢ ወንበርታ ተወላጆች የሆኑ የመንግስት ምልሻዎች የመንግስት አካላትን ከድተው ከህዝቡ ጎን ተሰልፈዋል (ከአንድ ምልሻ በስተቀር ሁሉም የአፅቢ ወንበርታ ምልሻዎች ከህዝቡ ጎን ይገኛሉ)። ሁለቱም ምልሻዎች (የአፅቢ ወንበርታና አስተዳደሩ ከሌላ ወረዳ ያስመጣቸው) ተፋጠዋል። አሁን 3: 15 በደራ ጣብያ ገብረኪዳን ልዩ ስሙ “አፅገበት” የሚባል ቦታ የነበሩ ወታደሮች (መከላከያ ሰራዊት) ባከባቢው ደርሰዋል። እስካሁን ምንም ዓይነት እርምጃ አልጀመሩም። ፀጥታ ሰፍነዋል። ህዝቡ ግን እንደተሰበሰበ አለ። “ተወካዮቻችን ፍቱልን” እያለ ይገኛል። አሁን ከምሽቱ 3:24 ነው።

ወታደሮቹ ህዝብ እንዲበተን ጥሪ አቀረቡ

በሰባት መኪኖች ሙሉ ተጭነው ወታደሮች ገብተው አከባቢው ተቆጣጥረውታል። “የዞን አስተዳዳሪዎች ነን” ያሉ ባለስልጣናት ህዝቡ “የአሸባሪነት ተግባር” እያከናወነ መሆኑ በርቀት ተናግረዋል። ህዝቡም “አሸባሪዎች እናንተ ናች ሁ፤ ልጆቻችን ፍቱልን” እያለ ሲጮህ ነበር። በመጨረሻም ወታደሮቹ ህዝቡ እንዲበተን ማስጠንቀቅያ ቢሰጡም አራቱ የአፅቢ ወንበርታ ልጆች ካልተፈቱ እንደማይበተን አስታውቀዋል። መከላከያውና አስተዳዳሪዎቹ ቢያስፈራሩም ህዝቡ ግን ለመበተን ፍቃደኛ አልሆነም። ዘጋቢዎቼ ወደ ቤታቸው እየተንቀሳቀሱ ነው። ነገ እንገናኝ። አሁን ከምሽቱ 3:55 ነው። ቸር ያሰማን።

አቡነ ማቲያስ ቤተ ክርስቲያኒቱን ከብዝበዛ በማዳን ታሪክ እንዲሠሩ ተጠየቁ

$
0
0

ሰንደቅ ጋዜጣ ከአዲስ አበባ እንደዘገበው፦

‹‹ዐይናችን፣ ጆሯችንና ልባችን የቤተ ክርስቲያናችንን ህልውና በሚወስነው የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ተግባራዊነት ላይ ነው፤ የቤተ ክርስቲያናችን ትንሣኤ ደርሷል ብለን እናምናለን፡፡›› /ምእመናን/

‹‹ከእውነተኛ የቤተ ክርስቲያኒቷ ጥቅም ወዲያና ወዲህ አልልም፤ አትጠራጠሩ! ሕጉ የጠራ ኾኖ በትክክሉ ይወጣል፤ ቤተ ክርስቲያናችን ወደቀደመ ክብሯ ትመለሳለች፡፡›› /ፓትርያርኩ/

‹‹የቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደር ከመሠረታዊው ተልእኮው ጋራ ያልተቀናጀ ከመኾኑም በላይ በወገንተኝነትና በሙስና የሚፈጸሙ የተለያዩ የሥነ ምግባር ብልሽቶች በስፋት የሚንጸባረቁበት ኾኖ ይስተዋላል፡፡ ይህን ከቤተ ክርስቲያኒቷ ክብርና ቅድስና ጋራ የማይጣጣም ሒደት ቅዱስ ሲኖዶሱ አስቸኳይ ርምጃ ሊወስድበት ይገባል፡፡ አስፈላጊው እርማት በወቅቱ ሳይደረግ በመቅረቱ፣ ምእመናኑ በቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር ላይ እምነት ማጣትን እያሳደረ ኹኔታውም እየተባባሰ ሲሔድ ይታያል፡፡ ስለዚህ ታሪክ እንዳይፈርድብን ካህናቱንና ምእመናኑን በማስተባበር አስቸኳይ የእርምት ርምጃ መውሰድ አስፈላጊ ይኾናል፡፡››

“እንደ አቡነ ጳውሎስ ነጭ ልብስ አልለብስም” – አቡነ ማቲያስ (ሙሉ ቃለ ምልልሱን ያድምጡ)
ይህ ጥቅስ አቡነ ማትያስ ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ኾነው ከተሾሙ በኋላ የመጀመሪያቸውን የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሁለተኛ ዓመታዊ ስብሰባ ግንቦት 22 ቀን 2006 ዓ.ም. በንግግር ሲከፍቱ ካሰሙት ቃል የተወሰደ ነው፡፡
ፓትርያርኩ ‹‹የቤተ ክርስቲያኒቱን ስም ለመጠበቅና የቀደመ ክብሯን ለመመለስ›› ሥር ነቀል የለውጥ ርምጃዎች እንደሚወስዱ ባስታወቁበት በዚያ የመክፈቻ ንግግራቸው÷ የቅ/ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ ብልሹ አሠራርን ለማረምና ለማስወገድ፣ አስተዳደሩን በአዲስ መልክ ለማዋቀርና ለፋይናንስ አያያዙ ዘመናዊነት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው አደረጃጀት ለመዘርጋት የሚያስችሉ ሦስት መሠረታዊ ርምጃዎችን እንደሚወስድ አመልክተው ነበር፡፡

አቡነ ማትያስ የቤተ ክርስቲያኒቱን ጤናማ ሒደት የሚወስኑ ናቸው ባሏቸው ሦስቱ መሠረታዊ ርምጃዎች ጋራ በተለይም ልዩ ሀገረ ስብከታቸው በኾነው በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት እየገዘፈና እየተመሰቃቀለ የመጣውን የመልካም አስተዳደር ዕጦትም በአደረጃጀቱና አሠራር ለውጥ ማስተካከል አስፈላጊ መኾኑን አሥምረውበት ነበር፡፡

ሓላፊነትና ተጠያቂነት ያለበት ግልጽ የአስተዳደር ሥርዐት የሚሰፍንበትን የለውጥ መሠረት በአስቸኳይ ማስቀመጥና አቅጣጫውን መቀየስ ‹‹በእግዚአብሔር፣ በታሪክና በመጪው ትውልድ ፊት›› ኹልጊዜ በሚዛን እየተመዘነ እንደሚኖር መዘንጋት እንደሌለበት ፓትርያርኩ ያሳሰቡት ለቅ/ሲኖዶሱ አባላት ጭምር ነበር፡፡

በስብሰባው መጨረሻ ግንቦት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ለብዙኃን መገናኛ ግልጽ የተደረገው የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ መግለጫ÷ በየቀኑ በለውጥ ጎዳና ከሚራመደው ዓለም በተሻለና በበለጠ መንፈሳዊና አእምሯዊ ጥበብ ሕዝበ ክርስቲያኑን ለመምራት፣ ለማስተማርና ለማገልገል ዕንቅፋት የኾኑ ችግሮችን በመለየት ዓበይት ውሳኔዎች መተላለፋቸው የተነገረበት ነበር፡፡ ከእነርሱም መካከል፣ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በመልካም አስተዳደር፣ በፋይናንስ አያያዝና በሰው ኃይል አመዳደብ የሕግ የበላይነትን አክብሮ የሚሠራበት የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ በቋሚ ሲኖዶሱና በፓትርያርኩ ጥብቅ ክትትል እንደሚደረግበት የሚያመለክተው ይገኝበታል፡፡

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ለሌሎች አህጉረ ስብከት በሞዴልነት የሚጠቀስበት ነው የተባለው የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናትም በፓትርያርኩ አባታዊ መመሪያ በተሰጠውና በሀ/ስብከቱ የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ኾነው በምልዓተ ጉባኤው ውሳኔ በተሾሙት አቡነ እስጢፋኖስ የቅርብ ክትትል በተደረገለት የባለሞያ ቡድን ተካሒዷል፡፡ 13 ጥራዞችና ከአንድ ሺሕ በላይ አጠቃላይ ገጾች ያሉት የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናቱ፣ በጥቅምት ወር በተካሔደው የቅ/ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ የመጀመሪያ ዓመታዊ ስብሰባ ላይ ሙሉ ይዘቱን በሚወክል ስላይድ ቀርቦ መገምገሙ ተገልጧል፡፡
ምልዓተ ጉባኤው በግምገማው፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሠረታዊ ተልእኮ ለኾኑት ክህነታዊና የስብከተ ወንጌል ተግባራት ቅድሚያ በመስጠት÷ ሥራና ሠራተኛን እንዲገናኝ፣ ደመወዝና ሞያ በሐቅ እንዲነጻጸር፣ ተቀባይነትና ተአማኒነት ያለው የገንዘብ ፍሰት እንዲኖርና የራስ አገዝ የልማት እንቅስቃሴ እንዲፋጠን ያስችላል ለተባለው የመዋቅርና አሠራር ጥናት ተግባራዊነት አቅጣጫ ሰጥቷል፡፡ ጥናቱ ወደታች ወርዶ በማኅበረ ካህናት፣ በማኅበረ ምእመናንና በሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶች ውይይት ዳብሮ፣ በውይይቱ በተገኘው ግብአት ተስተካክሎ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲቀርብና ቋሚ ሲኖዶሱም ዓይቶና ተመልክቶ በሥራ ላይ እንዲያውል ነው ምልዓተ ጉባኤው የሰጠው አቅጣጫ፡፡

ከትላንት በስቲያ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ገዳማትና አድባራት የተውጣጡና ከፓትርያርኩ ጋራ የተነጋገሩ ምእመናን ለአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናቱ ያላቸውን ድጋፍና ለተግባራዊነቱም የሚኖራቸውን አጋርነት ገልጸዋል፡፡ ሀ/ስብከቱ ከኅዳር 14 – ታኅሣሥ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ድረስ ቁጥራቸው ከ2700 በላይ የኾኑ አለቆችን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችን፣ ካህናትን፣ ሊቃውንትን፣ የሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶችንና ምእመናንን በአደረጃጀትና አሠራር ጥናት ሰነዱ ላይ ማወያየቱን የገለጹት ምእመናኑ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን መልካም ስምና ዝና ወደ ቀደመ የክብር ቦታው ለመመለስ የሚያስችል ነው ያሉት የአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ በቅ/ሲኖዶሱ ውሳኔ መሠረት በውይይቱ በተሰበሰበው ግብአት ተስተካክሎና በቋሚ ሲኖዶሱ ጸድቆ ተግባር ላይ እንዲውል ጠይቀዋል፡፡
ማንኛውም ለውጥ በተለይም የሥራ አመራር ለውጥ የራሱ ተግዳሮቶች እንዳሉት የተናገሩት ከደብረ ሲና እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን የመጡት የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ዮናስ፣ በአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ ጥቂቶች የሚያሰሙት ተቃውሞ መታየት ያለበት በትግበራ ሒደት በሚቋቋመው የቅሬታ ኮሚቴ መኾኑን አስረድተዋል፡፡ በለውጥ ሥራ አመራር ከተለመደው በተለየ ከትግበራ በፊት በመዋቅር፣ አደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናቱ የጎደለው እንዲሟላ፣ የጠመመው እንዲቃና ቤተ ክርስቲያኒቱ ዕድል መስጠቷን ሰበብ አስባብ እየፈለጉና ምክንያት እየለጠፉ ለውጠን ለማሰናከል የሚሞክሩ አካላት መኖራቸውን ገልጸዋል፡፡ ተቃዋሞው ለውጡን ከራስ ጥቅም አንጻር ብቻ ከመመልከት የሚመነጭ መኾኑን ያብራሩት አቶ ዮናስ፣ ‹‹የእኛን ልብስ ለብሰው እኛን መስለው የገቡ ተቃዋሚዎች እኛ ለልጆቻችን ለማስተላለፍ የምንፈልጋትን ቤተ ክርስቲያን አይወክሉም፤›› ብለዋል፤ በተቃዋሚዎቹ ግፊት የአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ በዐዲስ መልክ ለመገምገም የተላለፈው ውሳኔም በጥንቃቄና በጥልቀት እንዲታይ ፓትርያርኩን አደራ ብለዋል፡፡
የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናቱ ወጣቶችም ሽማግሌዎችም ወይዛዝርትም የሚስማሙበትና በቤተ ክርስቲያኒቱ የተንሰራፋውን የአስተዳደር ብልሽትና የገንዘብ ብዝበዛ እንደሚያስቆም ጽኑ እምነት እንዳላቸው የገለጹት ሌላው አስተያየት ሰጭ አቶ ከበደ ሙላት ከመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የመጡ ናቸው፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ ቃለ ዐዋዲ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1965 ዓ.ም. ሲረቀቅ ከአርቃቂዎቹ አንዱ እንደነበሩ የተናገሩት አዛውንቱ ምእመን አቶ ከበደ፣ ‹‹ዛሬ ያ ቃለ ዐዋዲና እኔ አርጅተናል፤ ጊዜው የሚጠይቀው አዲስ መዋቅር ያስፈልገናል፤ አዲስ መዋቅር ባለመኖሩ ምክንያት ቤተ ክርስቲያናችን ላይ ብዙ ጉዳት እየደረሰ ሲያንገበግበን ኖሯል፤›› በማለት የተሰማቸውን ቁጭት ገልጸዋል፡፡

የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ጥናቱ የተረቀቀው አዲስ መዋቅር በሚያስፈልግበት ወቅት መኾኑን የጠቀሱት አቶ ከበደ፣ በአስተዳደር ብልሽቱ ራሳቸውን ያበለጸጉ አካላት በለውጡ በሚቋረጥባቸው ሕገ ወጥ ጥቅም ክፉ ወሬ ማስወራታቸው አስገራሚ አይደለም ብለዋል፡፡ አያይዘውም ‹‹እንኳንስ ከቤተ ክህነትና ከቤተ መንግሥትም ቢኾን ለአገርና ለሕዝብ የሚጠቅም ነገር ሲነሣ ኹሉም እልል ብሎ አይቀበልም›› ያሉት አቶ ከበደ፣ ‹‹በኢትዮጵያ ምዕራፍ ውስጥ ለስምዎም ለታሪክዎም ብቅ ብሎ የሚታይ ነው›› ያሉትን የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ፓትርያርኩ ደፍረው እንዲያስፈጽሙትና ቤተ ክርስቲያኒቷን ከብዝበዛ በማዳን ታሪክ እንዲሠሩ ተማፅነዋቸዋል፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ነው አደራ የጣለብዎት፤ ሕዝቡም አደራ ጥሎብዎታል፤ ያንን ሕዝቡ የጣለብዎትን አደራ ከፍጻሜ ለማድረስ ብርታቱን ይስጥዎት፡፡››
የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ጥናቱ በሕይወት ያሉትም የሌሉትም በርካታ ምእመናን የጸሎትና እንባ ውጤት ነው ለማለት እንደሚደፍሩ የተናገሩት ወ/ሮ ቅድስት የተባሉ ምእመንት፣ በመንፈሳዊውም በሥጋዊውም ስለት በተሳሉ ባለሞያዎች የተዘጋጀ ነው ባሉት ጥናት ‹‹የቤተ ክርስቲያናችን ትንሣኤ ደርሷል ብለን እናምናለን፤›› ብለዋል፡፡ በጥናቱ የቤተ ክርስቲያኒቱን ችግር በሚገባ ማወቃቸውን ያስረዱት ወ/ሮ ቅድስት÷ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ የምእመኑ ዐይን፣ ጆሮና ልብ ለቤተ ክርስቲያን ህልውናና የቀረው ሕዝቧ እንዳይበተን ወሳኝ ነው ባሉት የጥናቱ ተግባራዊነት ላይ መኾኑን ገልጸዋል፤ ያለአንዳች ተቃውሞም በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲኾንም ፓትርያርኩን ጠይቀዋል፡፡

ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ምእመናኑ ለአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናቱ ተግባራዊነት ያላቸውን ስጋት በመግለጻቸው ደስ መሰኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡ አንድ የተወሰነ ቡድኑ ያጠናው የሕግ ረቂቅ ከቤተ ክርስቲያን ባህልና ቋንቋ አንጻር እንዲታይ መደረጉ ሕጉ የበለጠ እንዲጠራና እንዲጠነክር ያደርገዋል እንጂ እንደማያዳክመው በማረጋገጥ የዘመኑ ምሁራንና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያሉበት ኮሚቴ ዳግመኛ እንዲያየው መሠየሙን ለምእመናኑ አስታውቀዋል፡፡ የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ጥናቱ ከቀረበው ይዘት ተዳክሞና የቤተ ክርስቲያኒቱን ጥቅም የሚጎዳ ኾኖ ቢመጣ እንደማይቀበሉትም ለምእመናኑ በተደጋጋሚ ቃል ገብተዋል፡፡

‹‹ከዚኽም ከዚያም ይምጣ፤ ኹሉም የሚናገረውን አዳምጣለኹ፤ ኹሉም የሚናገረውን እያስተናገድኹ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ጥቅም ግን ወዲያና ወዲህ አልልም፤›› ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ፍላጎታቸው ቤተ ክርስቲያኒቱ ትክክለኛ መሥመሯን እንድትይዝ፣ ወደ ጥንቱ ቅድስናዋና ንጽሕናዋ እንድትመለስ በመኾኑ የአደረጃጀትና የአሠራር ጥናቱ ከደረሰበት ወደ ኋላ የሚመለስበት ምንም ምክንያት እንደማይኖርና ወደኋላ መመለስ ዘበት ነው ብለዋል፡፡ ‹‹አትጠራጠሩ! ምሁራኑም ይዩት፤ ሊቃውንቱም ይዩት፤ ሕጉ የጠራ ኾኖ በትክክሉ ይወጣል፤ ቤተ ክርስቲያናችን ወደ ቀደመ ክብሯ ትመለሳለች፤›› በማለት ለተግባራዊነቱ የምእመናኑን ድጋፍና እገዛ ጠይቀዋል፡፡

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live