Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

መማር እንችላለን ወይ? -አንዱዓለም ተፈራ

$
0
0

አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ

ረቡዕ፤ ሚያዝያ ፯ ቀን ፳፻፯ ዓመተ ምህረት ( 04/15/2015 )

eskemecheከ፲ ፱ ፻ ፷ ፮ ዓመተ ምህረቱ የየካቲት ሕዝባዊ መነሳሳት ጀምሮ፤ ለመብት፣ ለነፃነትና በሰላም ሠርቶ ለመኖር ያለው ትግል፤ ሳያርፍ በተከታታይ አሁንም እየተካሄደ ነው። በነዚህ ባለፉት ፵ ዓመታት፤ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን፤ በትግሉ ከሕዝብ ጎን ተሰልፈው ሕይወታቸውን ሠጥተዋል። ቆራጥ የሕዝብ ጠበቃዎች ወጥተዋል፤ ሕይወታቸውን ላመኑበት ዓላማ በቆራጥነት በመሥጠት በጀግንነት ተቆጥረዋል። ትውልድ አልፎ ትውልድ ተተክቷል። በግለሰብ ደረጃ፤ አጥንት የሚሰብሩ፣ ደም የሚነውጡ፣ ልብ የሚነኩ፣ አንጀት የሚያንሰፈስፉ፣ ጀግንነት የተሞላባቸው ተግባራት ተከናውነዋል። ድርጅቶች ተነስተዋል፣ ወድቀዋል። በድርጅቶች ደረጃ፤ ሕዝባዊ ጉዳዮችን መልክ ባለው መንገድ አመቻችተው ባደባባይ አውጥተዋቸዋል። አባሎቻቸው ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍለውበታል። መሪዎቻቸው ከፍተኛ መሯሯጥን የኑሯቸው ማዕከል አድርገው መርተውበታል። በወቅቱ በተደረጉት ክንውኖች ላይ ጽሑፍት ጎርፈውባቸዋል። ግጥሞች ተደርሰውባቸዋል። መጽሐፍት ታትመውባቸዋል።

አሁንም እንድትናንቱ ትግሉ ቀጥሏል። አሁንም የነበሩት ጥያቄዎች ባሉበት ቆመዋል። አሁንም መብት፣ የሀገር ሰውነትና በሰላም ሠርቶ መኖር ማዕከላዊ ጥያቄዎች ናቸው። ለምን ወደፊት መሄድ አልተቻለም? ለምን ትግሉ ባህልና ቋሚ ሆኖ አብሮን ይኖራል? ለዚህ መልስ መሥጠት ቀላል አይደለም። በአንድነት፤ በሀገር ደረጃ፤ እስካሁ ካደረግነው ትግል ምን ትምህርት እናገኛለን? የሚለውን በመፈተሽ፤ የመጀመሪያውን ወደ ስኬት ለመሄድ የሚደረግ እርምጃ፤ መራመድ እንችላለን። ይህ የግድ መደረግ አለበት። ባንድ ጽሑፍ፣ ባንድ ውይይት፣ ባንድ ትዕይንተ ሕዝብ፣ ባንድ ምሽት፣ ባንድ ግጥም አይከናወንም። ካለፈው ካልተማርን፤ ያለፈውን ባለፈው መንገድ መድገማችን አያጠራጥርም። ለዚህም ይኼው ፵ ዓመት ባስቆጠረውና እየቀጠለ ባለው ትግላችን፤ እያስመሰከርነው ነው። የሚቀጥለው እንዲስተካከል፤ ያለፈው መመርመር፤ በጎና በጎ ያልሆኑ ጎኖቹ ተለይተው መውጣት፤ አለባቸው። እናም ለኛ ትምህርቱ ቢያንስ አሁን መጀመር አለበት። እስኪ እኔም፤ ለዚህ ከፍተኛ ትኩረት ተሠጥቶት፤ በብዙዎች ብዙ መጻፍ ባለበት ጉዳይ ላይ፤ በኔ አመለካከት ምን ነበርና ምን ትምህርት እንወስዳለን የሚለውን ልነካካ።

የ፲ ፱ ፻ ፷ ፮ ዓመተ ምህረቱ የየካቲት ሕዝባዊ መነሳሳት የተከሰተው፤ የፖለቲካ ድርጅቶች በመድረክ ላይ በገሃድ ባልታዩበትና በአንድነት ተሰባስቦ የመታገል ልምዱ ባልዳበረበት ወቅት ነበር። በርግጥ የተማሪ ማኅበሩ፣ የአርሶ አደሮች በየቦታቸው በተደጋጋሚ ያደረጉት እንቅስቃሴ፣ አነስተኛ የነበረው የሠራተኛው ክፍል መነሳሳት፤ ለዚህ የ፲ ፱ ፻ ፷ ፮ ዓመተ ምህረቱ የካቲት ሕዝባዊ መነሳሳት ያለጥርጥር መሠረቱ ነበር። ትልቁ ክፍተት የነበረው፤ ሀገራዊ ራዕይ ይዞ፣ ታዋቂነትን አንግቦ፣ መዋቅር ዘርጎቶ፣ ልምድና ዝግጅትን አከማችቶ፣ በሕዝቡ ዘንድ መርኀ-ግብሩን አሰምቶ፣ በቦታው የነበረውን ሕዝባዊ መነሳሳት መሪ የፖለቲካ ድርጅት አለመኖሩ ነው። እናም ትክክለኛ ሕዝባዊ ጥያቄዎች የትግሉን አየር ሞልተው በተመሙበት ወቅት፤ የሕዝቡን መነሳሳት ቀዳዳ ተጠቅመው፤ ሥልጣን ወዳድ ወጣት መኮንኖች፤ ሕዝቡን አግልለው፣ ትግሉን አኮላሽተው፣ ሀገር ወዳድ ተማሪውን ፈጅተው፣ ሀገራችንን ደም በደም ለቃልቀው፣ የደም ጥማታቸውን ካረኩ በኋላ፤ በወራዳውና ሰው በላ አረመኔ መሪያቸው፤ በመንግሥቱ ኃይለማርያም አማካኝነት፤ ለአሁኖቹ ተረኛ ተባዮች አስረከቡን። በዚህ ደርጋማ መንግሥት ዘመን ትግሉ ምን መልክ ያዘ? በዚህ ወቅት ሌሎች ምን ያደርጉ ነበር? ምን እንገነዘባለን ነው ከወቅቱ የምናገው ትምህርት።

በወቅቱ ዋነኛ ተጫዋቾች ከነበሩት የትግል ድርጅቶች መካከል፤ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ ( ኢሕአፓ )፣ የመላ ኢትዮጵያዊያን ሶሺያሊስት ንቅናቄ ( መኢሶን )፣ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኅብረት ( ኢዲዩ )፣ ተጋድሎ ሓርነት ኤርትራ   ( ተሓኤ – ጀብሃ )፣ ሕዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ ( ሕግሓኤ – ሸዓቢያ )፣ የኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር ( ኦነግ )፣ የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጪ ግንባር ( ትሕነግ – ህወሓት – ወያኔ )፣ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (ትነግ – ጠርናፊት )፤ የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር ( ኦብነግ )፤ ነበሩበት። የኤርትራ ታጋይ ድርጅቶችን በነበሩበትና ባሉበት እተዋቸዋለሁ። ቀሪ ነፃ አውጪ ግንባሮችን ደግሞ፤ – ኦነግ፣ ትነግ፣ ኦብነግ – ነፃ ለመውጣት ያደረጉት ትግል ነበርና፤ እንደ ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች ልተቻቸውና ትግላቸውን ልመረምር መረጃውም ሆነ የሞራል ፍቃዱ የለኝም። በርግጥ የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጪ ግንባርን ( ትሕነግ – ህወሓት – ወያኔ ) በሚመለከት፤ ብዙ የምለው አለኝ። ለምን? የሚለው ጥያቄ ከተነሳ፤ ከነፃ አውጪነቱ ወጥቶ ኢትዮጵያን በሙሉ ወሮ በአምባገነንነት እየገዛ ነውና!

በወቅቱ የነበሩት ድርጅቶች፤ ሲነሱ ሁሉም ዴሞክራሲ፣ ነፃነት፣ መብት፣ ሕዝባዊ ተሳትፎ፣ እኩልነት በማለት ነበር። የትግል ዓላማቸው፣ ግባቸውና ዘዴያቸው ምን ነበር? ለምን አልተሳካላቸውም? እኒህ ናቸው በአንድነት በሀገራዊ መልኩ መታየት ያለባቸው ጉዳዮች። ጎልቶ በትግል መድረኩ ላይ ከፍተኛ ሚና በተጫወተውና በመጠኑም ቢሆን አውቀዋለሁ በምለው በኢሕአፓ ልጀምር።

ኢሕአፓ፤ በተማሪው ትግል ዋናውን ሚና ይጫወቱ የነበሩ ወጣቶች፣ በተማሪ ትግሉ መሪና አስተባባሪ የነበሩ ወጣቶች፤ በተለይም በውጭ ሀገር የነበሩ ታጋይ ተማሪዎችና በሠራተኛው ክፍልም የሠራተኛውን እንቅስቃሴ ይመሩና ያቀናጁ የነበሩ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ያቋቋሙት ፓርቲ ነበር። በትምህርት ዓለም ውስጥ ያጠኑትን የዓለም የፖለቲካ ሂደትና የተገነዘቡትን የፖለቲካ አሰላለፍ በመመርመር፤ በወቅቱ በነበረው የሶስተኛው ዓለም የነፃነት ንቅናቄና በሶቪየት ኅብረት የቅኝ ግዛቶች ድጋፍ በመመሰጥ፤ የሶሺያሊዝም አቀንቃኝነቱን ወስደው፤ ኮሚኒዝም ከነበርንበት አዘቅት የሚያወጣ መፍትሔ ብለን በመውሰድ፤ ትግሉን የሶሺያሊስት ንቅናቄ አድርገን ተነሳን። በወቅቱ የተነሱት ጉዳዮች፤ ማለትም የዴሞክራሲ መብቶች አለመከበር፣ የደሃ ልጅ የትምህርት ገበታ ዕድሉ መነፈጉ፣ ሕክምና ወደ ገጠር አለመዛመቱ፣ የሴቶች በእኩልነት በኅብረተሰቡ አለመገኘት፣ መሬት በጥቂት የመሬት ባለቤቶች ተይዞ ጢሰኛው ባላባቱ በፈቀደለትና በፈቀደው መንገድ የሚነዳው እስረኛ መሆኑ፣ የመሬቱ ባላባት የሆነው የገዥው መደብ አባልና በመሬቱ የሚለፋው ጢሰኛ፤ የትውልድ ሀረጋቸው አንድ አለመሆኑና ቋንቋቸው የተለያየ መሆኑ በሀገሪቱ ያስከተለው የመበላለጥ ልዩነት፣ የሃይማኖቶች በእኩልነት አለመመዘን፣ የሠራተኛው ክፍል በሕግ የሚተዳደርበት ትክክለኛ አሠራር አለመኖሩ፣ የግብር አሰባሰቡ አርሶ አደሩን መበደሉ፤ እኒህ ሁሉ ትክክለኛ ጥያቄዎች ነበሩ። እኒህን በማንሳትና ኮምኒዝምን በማወጅ መካከል የነበሩትን ደረጃዎች በሽምጥጥ በማለፍ የተደረገው ጉዞ፤ ተሰናከለ።

በአንጻሩ ደግሞ፤ ይህ በፖለቲካ ትግል ሂደቱ የተፈጠረው የኢሕአፓ ፓርቲ፤ የሚመረኮዝበት ኢትዮጵያዊ ታሪኩም ሆነ ልምዱ ስላልነበረው፤ መነሻና መድረሻ አድርጎ የወሰደው የሌሎች ሀገር ተመክሮዎችን ነበር። እናም፤ በወቅቱ በሀገራችን የፖለቲካ ሀቅ ላይ የተመረኮዘ መፍትሔ ሳይሆን፤ ሌሎች ያራምዱት የነበረውን የሶሽያሊስት መርህ ተጠቅሞ፤ ከሀገራችን ጋር ባልተቀናጀ መንገድ ለመተግበር ተነሳ። የድርጅቱ ድክመት፤ ፍላጎቱና ጥረቱ ሳይሆን፤ የተጨባጭ ሁኔታውና ያደረገው ጥረት አለመጣጣም ነው። ፍጹም ኋላቀር በሆነች ሀገራችንና የላበደሩ ቁጥር ከዚህ ግባ በማይባልበት ደረጃ በነበረበት ወቅት፤ የሶሻሊዝምን ሥርዓት ለማንገሥ የተነሳው ኢሕአፓ፤ መሠረቱና ዕድገቱ በወጣት የከተማ ተማሪው ላይ ነበር። ይህ ክፍል በቆራጥነት ሕይወቱን ለትግሉ ሠጠ። ደርግ ደግሞ አረመኔነት በተሞላ አሰቃቂ መንገድ ይኼን ወጣት በላው። የዚህ ፓርቲያችን ተመክሮ ባጭሩ እንዲህ ነበር።

በወቅቱ በቦታው ሊያሳድገው የሚችለውን ኢትዮጵያዊ ሂደት ሳይከተል፤ በፍላጎቱ ላይ ብቻ ተመስርቶ ያደረገው ግስጋሴ፤ ውስን ሆኖ ቀረ። የድርጅት መሪዎች ዋና ተግባር፤ ወቅታዊ ለሆነው ጉዳይ ወቅታዊ የሆነ መልስ አዘጋጅተው፤ ተከታዮቻቸውን መምራት ነው። ለነበረው የፖለቲካ ጉዳይ፤ በኢሕአፓ አመራር የተሠጠው ትንታኔና መፍትሔ፤ ደረጃውን የጠበቀና ወቅታዊ አልነበረም። በርግጥ የደርግ በዚህ ድርጅት ላይ የተለየ ትኩረት ማድረጉና የህወሓት ሆን ብሎ ይኼን ድርጅት ለማጥፋት ያደረገው ጥረት ቀላል አልነበረም። ድርጅቱ፤ ዓላማው ላለመሳካቱ ምክንያት ፍለጋ ወደ ውጪ መመልከት የለበትም፤ ዋናው ምክንያት ከውስጥ ነበር። ወሳኝ የነበረው ውስጣዊ ማንነቱ ነበር። የመርኅ መሠረቱና የአመራሩ ችሎታ በቦታው አልተገኙም። እናም ድርጅቱ ሳይሳካለት ቀረ።

የመላ ኢትዮጵያዊያን ሶሺያሊስት ንቅናቄ ( መኢሶን ) እንደ ኢሕአፓ ከተማሪው እንቅስቃሴ የበቀለ ንቅናቄ ነበር። በዚያ ውስጥ ግን የሥልጣን ጥማቱ ያናወዛቸው ግለሰቦች ተሰግስገውበት ስለነበር፤ በአቋራጭ ሥልጣን ለማግኘት፤ ተሽቀዳድመው ቤተ መንግሥት በመግባት፤ የደርግ አገልጋይ ሆኑ። ደርግን ተጠቅመን እንነግሣለን ሲሉ፤ ደርግ እንሱን የኢሕአፓ መግደያ መሣሪያ አድርጎ፤ የተማሪውን መከፋፈያ አድርጎ፤ የደሙ መጥረጊያ ጨርቅ አድርጎ ቀደማቸውና፤ ሰለባቸው። ከመኢሶን ከዚህ የበለጠ የምንማረው ያለ አይመስለኝም።

የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኅብረት ( ኢዴኅ – ኢዲዩ ) የፖለቲካ መርኀ ግብሩ ዴሞክራሲያዊ እያለ ቢያትትም፤ ከፖለቲካ መስመር ይልቅ፤ ፀረ-ወታደር በመሆን የድሮውን ለመመለስ በችኮላ የተቋቋመ ድርጅት ነበር። በርግጥ የድሮውን የወደዱና የወታደሩን ያለቦታው ዙፋኑ ላይ መቀመጥ ያልተቀበሉ፤ ጄኖራሎች፣ ሀገረ ገዥዎች፣ መሳፍንታትና አምባሳደሮች በችኮላ ተቀላቅለውታል። ከዚያ ያለፈ ግን መርኀ-ግብሩን ተረድተውና ለዓላማው በመቆም የተሰለፉ የነበሩ አይመስለኝም። ባጭር ጊዜ ለነበረው እድገታቸው ተመጣጣኝ አመራር ሠጪ አካልና ማዕከላዊ አሰራር ስላልነበራቸው፤ ከደርግም ሆነ ከሌሎች ታጋይ ድርጅቶች በገጠማቸው ተቃውሞ ተመናምነው ጠፉ። ከዚህ በላይ ስለ ኢዴኅ ማለት አልችልም።

የቀረው የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጪ ግንባር ( ትሕነግ – ህወሓት – ወያኔ ) ነው። ከአፄ ዮሐንስና ከትግራይ መሳፍንት ጋር የተያያዘው የትግራይ ወጣቶች የነፃነት ግንባር፤ ምንም እንኳ ከተማሪ ማኅበሩ የመጡ መሪዎችና ተከታዮች ቢኖሩበትም፤ ከጠባብ የትግራይ መሳፍንት ገዥነት ጋር የተያያዘ የነፃነት ትግል ነበር። ስለዚህ ይህን ግንባር ከተማሪ ትግሉ ጋር ማዛመድ ስህተት ነው። የዚህ ነፃ አውጪ ግንባር መሠረቱ የትግራይ ሪፑብሊክን መመሥረትና የአማራ ገዥነትን ማጣፋት ነው። በምንም መንገድ ከማርክሲዝምና ከላብ አደሩ አምባገነንነት ጋር ግንኙነት የለውም። ይህ ትግራይን ነፃ አድርጎ የራሷ ሀገር የመፍጠር ጉዳይ፤ ኢትዮጵያዊ ያልሆነ፣ ከሀገር አቀፉ እንቅስቃሴ የተለየና በተቃዋሚነት የቆመ ነበር። ስለዚህም፤ ህወሓት በጠላትነት የፈረጃቸው፤ ደርግን ብቻ ሳይሆን፤ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (ትነግ – ጠርናፊት )ን፣ ኢሕአፓን እና አማራን ነበር፤ አሁንም ነው። የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (ትነግ – ጠርናፊት )ን ስላጠፋው ከቁጥር አስወጥቶታል። ኢሕአፓን በሚችለው መንገድ ወግቶታል። አማራውን አሁንም በማጥፋት ላይ ነው። የዚህ ድርጅት ተግባር ሕዝባዊም፤ ኢትዮጵያዊም አይደለም። ከዚህ የምንማረው ቢኖር፤ ይህ ድርጅት መጥፋት እንዳለበትና ይህም ባስቸኳይ መሆን እንዳለበት ነው።

ለመንደርደሪያ ያህል ይኼን ካስቀመጥኩ በኋላ፤ አጠቃላይ በሆነ መልኩ ወደፊት የሚመለከት መፍትሔ በመጠቆም፤ ጽሑፌን አስራለሁ። የ፲ ፱ ፻ ፷ ፮ ቱ ህዝባዊ እንቅስቃሴ መሠረታዊ ጥያቄዎች፤ ዴሞክራሲያዊ መብቶች ይከበሩ፣ መሬት ለአራሹ ይሁን፣ የሴቶች እኩልነት ይከበር፣ ሃይማኖት የግል ስለሆነ፤ መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ አይግባ፣ ሁሉንም ሃይማኖቶች እኩል ይመልከት፣ ሕክምና በገጠር ይስፋፋ፣ የድሃ ልጅ ይማር፣ ለተራበው ወገናችን እርዳታ ይደረግለት፣ የገዥዎች ያላአግባብ በሀብት ማላገጥ ይቁም፣ የኑሮ ውድነት ይስተካከል፣ ለሠራተኛው ትክክለኛ ሕግ ወጥቶ በሕገ-ደንብ ይስተዳደርና የመሳሰሉት ነበሩ። እኒህ ሀገራዊ ጥያቄዎች ነበሩ። አሁንም አሉ። አሁንም ሀገራዊ ጥያቄዎች ናቸው። በአንድነት ተነስተን በአንድነት ለማስከበር የምንቆምላቸው ነበሩ። ያኔ አልተደረገም። አሁንም እየተደረገ አይደለም።

የያዝነው ትግል ውጤቱ እንዲቃና፤ እስካሁን ከተደረገው ትግል ተምረን፤ ትግሉን በተስተካከለ መንገድ ማካሄድ አለብን። ጥያቄዎቹ ቀለም ይቀቡና ሌላ መልክ ይያዙ እንጂ እኒሁ ናቸው። ተጎጅው ደግሞ ያው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። ትግሉ የሕዝቡ ነውና የሕዝቡን ባለቤትነትና የበላይነት መቀበል ዋነኛ መሠረታዊ ግዴታ ነው። ቀጥሎ ደግሞ፤ ያለውን የሀገራችንን የፖለቲካ እውነታ በትክክል ተንትኖ፤ ለዚህ ወቅታዊ የፖለቲካ ሀቅ ትክክለኛ መፍትሔ ማቅረቡ ነው። በኔ እምነት፤ በኢትዮጵያ ያለው ወራሪ መንግሥት ነው። ይኼን ወራሪ መንግሥት መታገል ያለብን፤ ጥቂት መሠረታዊ የሆኑ ሀገራዊ የትግል ዕሴቶችን በማውጣት፤ አንድ የኢትዮጵያዊያን ሕዝባዊ የነፃነት ንቅናቄ መሥርተን በመነሳት ነው። መታገያ ዕሴቶቻችን፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነት መከበሩ፣ የኢትዮጵያ ሀገራችን ዳር ደንበር መጠበቁ ለሙ መሬቷ ለኢትዮጵያዊያን መዋሉ፣ የያንዳንዳችን ኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ መብት መከበሩ፣ እና የሕግ የበላይነት መረጋገጡ ናቸው። በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ያለነው በአንድነት በነዚህ ሀገራዊ አንገብጋቢ ዕሴቶቻችን ዙርያ በመሰባሰብ መነሳት አለብን።

ከነዚህ አንገብጋቢ ዕሴቶቻችን ውጪ ያለው ጉዳይ፤ በመሠረቱ የሕዝቡን የትግሉ ባለቤትነትና የበላይነት እስከተቀበልን ድረስ፤ በሂደት ሕዝቡ በትግሉ ስለሚያነሳቸውና መፍትሔ ስለሚሠጣቸው፤ ላሁኑ በቆይታ ይታያሉ። እናም በነዚህ ዙርያ ተጠማጥመን እንቅስቃሴውን በአንድነት በአንድ ድርጅት ከውጪ ያለነው እናካሂደው። ካለፈው እንማርና፤ ለዚሁ አንድ ጉዳይ፤ ባንድ ተሰልፈን፤ ቆመን እንቆጠር። መማር ማለት፤ ከትናንት ተሽሎ መገኘት ማለት ነው። መማር ማለት ባሉበት መርገጥ ማለት አይደለም። መማር ማለት ማደግ ማለት ነው።

The post መማር እንችላለን ወይ? -አንዱዓለም ተፈራ appeared first on Zehabesha Amharic.


በሞያሌ ሕወሓት የሚመራው መንግስትን ይደግፋሉ የተባሉ ንግድ ድርጅቶች ውድመት ደረሰባቸው

$
0
0

በሞያሌ በተነሳው ተቃውሞ ከገዢው ፓርቲ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ ሆቴሎች ከፍተኛ ውድመት ደረሰባቸው
ኢሳት ዜና :- የከተማ ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጹት በከተማዋ ከሚታወቁት ሆቴሎች መካከል ፈቃዱ ሆቴል ፣ ኢትዮ ኬኒያ ሆቴል ፣ ሃጎስ ሆቴልና ማሕሌት ሆቴል ጉዳት ድርሶባቸዋል።

Moyale Main Street (Photo file)

Moyale Main Street (Photo file)


የሆቴሉ ባለቤቶች የገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ናቸው በሚል ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ነዋሪዎች ተናግረዋል። በተለይ ኢህአዴግን በመደገፍ እና ቅስቀሳ በማድረግ የሚታወቁት የማህሌት ሆቴል ባለቤት ንብረት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል። የአካባቢው ሽማግሌዎችና የጎሳ መሪዎች የተጎዱ ሆቴሎችን የጎበኙ ሲሆን ፣መረጋጋት እንዲፈጠር ነዋሪዎች ለማሳመን እየጣሩ ነው።

ከሞያሌ ወጣብላ በምትገኘው ኩሌንሳ መንደር የተኩስ ድምጽ መሰማቱን የገለጹት ምንጮች፣ ውጥረቱ አሁንም ድረስ እንዳለ ተናግረዋል። በመከላከያ ሰራዊት አባላትን በሶማሊ ክልል ታጣቂዎች መካከል የተነሳው ግጭት በፌደራል ፖሊሶች ጣልቃ ገብነት ቢበርድም፣ በማንኛውም ጊዜ ሊነሳ ይችላል በሚል ነዋሪዎች ስጋታቸውን ገልጸዋል። ትምህርት ቤቶች፣ የመንግስት መስሪያ ቤቶችና አንዳንድ ድርጅቶች ዛሬ መከፈታቸውን ለማወቅ ተችሎአል።

The post በሞያሌ ሕወሓት የሚመራው መንግስትን ይደግፋሉ የተባሉ ንግድ ድርጅቶች ውድመት ደረሰባቸው appeared first on Zehabesha Amharic.

(የቡና ቁርስ) በዚህ ሳምንት የተማርናቸው ሦስት ነገሮች * ኬንያም ኢትዮጵያም ሽብርተኝነት ላይ ሚዛን ስተዋል * ዶናልድ ሌቪን የኔታ ናቸው * ድምጻችን ይሰማ ብርቱ ነው

$
0
0

1ኛ) ኬንያም ኢትዮጵያም ሽብርተኝነት ላይ ሚዛን ስተዋል 

ከሁለት ዓመት በፊት ዘ-ኢኮኖሚስት መጽሔት ጎረቤታሞቹ ኢትዮጵያ እና ኬንያ በሚከተሏቸው የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ አስተዳደር ሞዴሎች መካከል ያለውን ልዩነት የሚገልጽ ጽሑፍ አስነብቦን ነበር። ጽሑፉ የሚጀምረው ሁለት የድንበር ከተሞችን በማነጻጸር ነበር፤ መተማን እና የኬንያ ሞያሌን። በመተማ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ጥብቅ በኾነ የፍተሻ ሂደት ውስጥ ማለፍ ግድ ይላል። ድንበር ጠባቂዎቹ የተጓዦች ፓስፖርቶችን በእጅ ጽሑፍ ከተጻፈ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ የተከለከሉ ሰዎችን ስም ዝርዝር ከያዘ ዶክመንት ጋራ ያመሳክራሉ። ፓስፖርቶቹ የሐሰት እንዳልኾኑ በጥንቃቄ ይመረምራሉ፤ ግልምጥምጥ እያደረጉ እና ኮስተርተር እያሉ ጥያቄ ይጠይቃሉ። በሞያሌ በኩል ወደ ኬንያ ለመግባት ግን ይህ ሁሉ ጣጣ የለም። የደንህንነት መኮንኖቹ ፓስፖርት ሲመለከቱ ፈታ፣ ዘና ብለው ነው። ጥበቃው ልል ከመኾኑ የተነሳ “የድንበር ፍተሻ ሳይኾን የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ይመስላል” ይላል ዘ-ኢኮኖሚስት። የኢትዮጵያ የአስተዳደር ሞዴል መተማን ይመስላል፤ መንግሥት ሁሉ አወቅ የኾነበት እና ከዳር እስከ ዳር ሥልጣኑንና ቁጥጥሩን ያረጋገጠበት። የኬንያ መንግሥት በተቃራኒው የቁጥጥር ድክመት ያለበት እና ክፍትነት የሚታይበት ነው።

BEN CURTIS, FILE — AP Photo Read more here: http://www.adn.com/2013/10/10/3119796/africa-vs-icc-quotes-on-court.html#storylink=cpy

BEN CURTIS, FILE — AP Photo
Read more here: http://www.adn.com/2013/10/10/3119796/africa-vs-icc-quotes-on-court.html#storylink=cpy

ባለፈው ሳምንት በጋሪሳ 147 ሰዎች ያለቁበትን የሽብር ጥቃት ተከትሎ በእነዚህ ሁለት ተቃራኒ ሞዴሎች ጉዳይ ክርክር ተጀምሯል። በኬንያ እንዲህ ዐይነት የሽብር ጥቃት ሲፈጸም የመጀመርያው አይደለም። በተቃራኒው በኢትዮጵያ ከ1999 ዓ.ም በኋላ መጠነ ሰፊ የሽብር ጥቃት አልተፈጸመም። አልሸባብ ሁለቱንም አገሮች (በተለይ ደግሞ ኢትዮጵያን) እንደ ከባድ ጠላት ይመለከታል። ነገር ግን የኬንያ ስኬቱን በኢትዮጵያ ሊደግመው አልቻለም። ይህን ያስተዋሉ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያን የአስተዳደር ሞዴል አንቆለጳጵሰውታል። እንዲህ ያሉ ክስተቶችን ተገን አድርገው ቋጥኝ የሚያካክሉ መደምደሚያዎች ላይ የሚደርሱ ሙግቶችን እና ትንተናዎች (ad hoc reasoning) ፋይዳ አነስተኛ ነው። ሲስተሞችን እና ሞዴሎችን በርትዕ እንዳንማር ያደርጉናል። ትልቁን ሥዕል እንዳንመለከት ዐይኖቻችንን ይጋርዷቸዋል። ይልቁንስ የሞዴሎችን ብቃት ለማወቅ መለኪያዎችን አውጥቶ መገምገም የተሻለ መንገድ ነው።

የፖለቲካ ፈላስፋዋ ሴይላ ቤን ሃቢብ ውስብስብ የፖለቲካ ማኅበረሰቦች አራት እሴቶች እንዳሏቸው ያስቀምጣሉ፤ ሌጂትሜሲ፣ የኢኮኖሚ ዋስትና፣ ደኅንነት እና አመክኗዊ የጋራ ማንነት። እነዚህ ግቦች በብዙኀኑ የፖለቲካ ማኅበረሰቦች አባላት የሚደገፉ ናቸው፤ በትርጉማቸው እና በይዘታቸው ላይ በየማኅበረሰቡ ጠንካራ ሙግቶች እና ያለ መስማማቶች ቢኖሩም። እነዚህ ግቦች እርስ በእርሳቸው የተወሳሰበ መስተጋብር አላቸው። አንዱን በተትረፈረፈ ኹኔታ ማግኘት ሌላውን ሊያሳጣ ይችላል። ለምሳሌ፦ ሌጂትሜሲን ለማምጣት እጅግ ክፍትና ነጻ የኾነ ሥርዐት ፈጥረን ደህንነትን አደጋ ላይ ልንጥል እንችላለን። የኢኮኖሚ ዋስትናን ለመጨመር ደግሞ የሰዎች ነጻነት ላይ ከመጠን ያለፈ ገደብ እናስቀምጥ ይኾናል። የጋራ ማንነታችንን ለማጠናከር ውህዳንን (minorities) እንጨቁናለን። የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሞዴሎች ብስለት እና ብቃት የሚለካው እነዚህን አራት እሴቶች አመዛዝኖ በማቅረብ ችሎታቸው ነው። በእነዚህ መለኪያዎች እንደ ኢትዮጵያ ያለ እጅግ ጣልቃ ገብና ሁሉን ዐወቅ መንግሥት በሳል ነው ለማለት ያስቸግረናል። ሕዝቡን መንግሥታዊ ካልኾነ ሽብር ለመጠበቅ ቢችልም፤ ይህን የሚያደርገው ሌጂትሜሲን እና የጋራ ማንነትን አደጋ ላይ በመጣል ነው። ለምሳሌ በ1999 ዓ.ም በኦጋዴን የተፈጠረውን ክስተት እናንሳ። የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር ታጋዮች በቻይና የነዳጅ ኩባንያ ላይ ጥቃት ፈጽመው 74 ሠራተኞችን ገደሉ፤ ብዙ ንብረት አወደሙ። የኢትዮጵያ መንግሥት በአጸፋው ለሦስት ዓመታት ሳያሰልስ የቀጠለ መሬት አንዳጅ፤ ጅምላ ጨራሽ ወታደራዊ እርምጃ ወሰደ። በርካታ የኦጋዴን ነዋሪዎች ተገደሉ፤ ተገረፉ፣ ተሰቃዩ፣ ቀያቸውን ለቀው ተሰደዱ። ይህ ጥቃት ኦብነግን ቢያሽመደምደውም የኦጋዴን ነዋሪዎችን መብቶች ክፉኛ የጣሰ እና ኢትዮጵያዊ ማንነታቸውን የበለጠ እንዲጠይቁ ያደረገ ነበር። አራቱን እሴቶች የሚያመዛዝን ሳይኾን ወደ አንዱ እሴት በእጅጉ ያዘነበለ ጥቃት ነበር። የተከፈለው ዋጋ የፖለቲካ ማኅበረሰባችንን አናግቷል። ኬንያ ከኢትዮጵያ በተቃራኒ ጫፍ ላይ ያለ የራሷ የኾነ አመዛዝኖ የማቅረብ ችግር አለባት። ለብሔራዊ ደህንነት የምትሰጠው ዋጋና ክብር አነስተኛ ነው። በኬንያ ላይ ጣታቸውን የቀሰሩ ኢትዮጵያውያን ይህን በሚገባ አብራርተውታል። ችግሩ ሦስቱ ጣቶቻቸው ወደራሳቸው እንደሚጠቁሙ መዘንጋታቸው ነው።

2ኛ) ዶናልድ ሌቪን የኔታ ናቸው

ታላቁ አሜሪካዊ የፖለቲካ ፈላስፋ ጆን ሮውልስ ከወጥ ሥራዎቹ በተጨማሪ በአንድ ነገር ይታወቃል፤ በየኔታነት (mentorship)። ለተማሪዎቹ የቅርብ ጓደኛ ኾኖ ሥራቸውን መከታተል እና ማበረታታት እንደ ምሁራዊ ግዴታው ይመለከት ነበር። ይህ ጠባዩ በርካታ ድንቅ ፈላስፎችን እንዲፈጥር ከማስቻሉም በተጨማሪ ተክለ ሰብእናውን እና ምሁራዊ ብቃቱን የሚያበስሩ ደቀ መዛሙርት እንዲያፈራ አድርጎታል። የምሁራን ስኬት በሥራቸው ብቃት ብቻ ሳይኾን በሌሎች ምሁራን ዘንድ ባላቸው ማኅበራዊ ካፒታል (social capital) ይወሰናል። ባለፈው ሳምንት በሞት የተለዩን የኢትዮጵያ ጥናቶች ታላቅ ሊቅ አሜሪካዊው ሶሲዮሎጂስት ዶናልድ ሌቪን ይህን እውነታ በሚገባ የተረዱ ነበሩ።

Oromo Narrative: Professor Donald Levineፕሮፌሰር ሌቪን በኢትዮጵያ ላይ የጻፏቸው ሁለት ታላላቅ መጻሕፍት ከታተሙ ቢያንስ አርባ ዓመታት አስቆጥረዋል። ከዚያ በኋላ የእርሳቸውን ሥራዎች የሚያፈርሱ እና በጥብቅ የሚሄይሱ ጥናቶች ታትመዋል። የተሻሉ ቲዮሪዎች እና ኢምፔሪካል ግኝቶች ተከትለዋል፤ የኢትዮጵያ ጥናቶች አድገዋል፤ ተመንድገዋል። መጻሕፎቻቸው በብዙ ወጣት ምሁራን ሥራዎች ውስጥ ቢጠቀሱም ሌቪኒዝምን አልፈጠሩም። በተጨማሪም ፕሮፌሰር ሌቪን ከምሁራዊ ሥራቸው አልፈው በኢትዮጵያ ፖለቲካ መጀመርያ ንጉሡን የሚቃወሙ ኀይሎችን በመርዳት በኋላም የቅንጅት ታሳሪዎች እና ኢሕአዴግን ለማደራደር በሽማግሌነት ያደረጓቸው ጥረቶች ያልተሳኩ ነበሩ። በተለያዩ ጊዜያት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ኢኮኖሚ ላይ የጻፏቸው መጣጥፎች ብዙም ተቀባይነት አላገኙም፤ እንዲያውም ከአንዳንዶች ጠንካራ ትችት ተሰንዝሮባቸዋል። ይኹንና በዶናልድ ሌቪን ሞት ተቺዎቻቸውን ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን ምሁራን ከልብ የመነጨ ሐዘናቸውን ሲገልጹ ሰንብተዋል። እነዚህ ምሁራን የሦስት ትውልድ አባላት ናቸው። አብዛኞቹ በሐዘን መግለጫቸው ከሌቪን አካዳሚያዊ ሥራዎች በተጨማሪ ከፕሮፌሰሩ ጋራ የነበራቸውን የጓደኝነት እና የተማሪ -መምህር ግንኙነት አንስተዋል። ሌቪን ከወጣት እስከ አዛውንት ከምሁራን ጋራ በመቀራረብ፣ ሳይታክቱ የደብዳቤ እና የኢ-ሜይል ልውውጦችን በማድረግ የድጋፍ ደብዳቤዎችን በመጻፍ፣ በአካዳሚያዊ ኮንፈረንሶች እና ሌሎች የትምህርት አውድማዎች በመገኘት ተፈንክቶና ተዘርዝሮ የማያልቅ ማኅበራዊ ካፒታል አዳብረዋል። ይህ ካፒታል የፖለቲካ ስህተት ሲሠሩ ሳይቀር ስማቸውን ከሚያበሻቅጥ ጥቃት እና ዝቅ አድርጎ ከሚያይ አስተያየት ጠብቋቸዋል። የኔታ ሊበን አፈር ይቅላለቸው።

3ኛ) ድምጻችን ይሰማ ብርቱ ነው

በአምባገነን ሥርዐቶች መንግሥታት ላይ ግፊት የሚያደርጉ ማኅበራዊ ንቅናቄዎች ዕድሜ እጅግ አጭር ነው። ከምሥረታቸው አንስቶ የማኅበራዊ ድርጊት ችግሮች (collective action problems) ይገጥሟቸዋል። መንግሥት ሰርጎ ገቦችን ያዘልቅባቸዋል፤ መሪዎቻቸው እና አባሎቻቸው ይታሠራሉ፤ ተለጣፊ ቡድኖች ይፈጠሩባቸዋል። በአጠቃላይ በእነዚህ ንቅናቄዎች ውስጥ የመሳተፍ ዋጋ (cost of participation) ይሰቀላል። ብዙዎች ተስፋ ቆርጠው ንቅናቄውን እንዲተዉ ያደርጋል፤ ዋጋ ሳይከፍሉ ስኬት መካፈል የሚፈልጉ ሰዎችን (free riders) ያበራክታል። ማኅበራዊ ንቅናቄዎች ከተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች በበለጠ ለእንደዚህ ዐይነቶቹ የአምባገነን መንግሥት ጥቃቶች የሚጋለጡባቸው የተለያዩ ምክንያቶች አሉ። ማኅበራዊ ንቅናቄዎች የአይዲዮሎጂ ጥራት እና ጥልቀት ይጎድላቸዋል፤ ከፖለቲካ ፓርቲዎች የበለጠ ሰፊ እና ልል ናቸው፤ አባላቶቻቸውን የሚያጣሩበት ወንፊት ዘርዘር ያለ ነው። ይኼን ሁሉ ግምት ውስጥ ስናስገባ ከአራት ዓመታት በላይ የቆየው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ድማጻችን ይሰማ ንቅናቄ ቀጣይነት ያስገርማል።

yisemaድምጻችን ይሰማ እንደ ብዙ ማኅበራዊ ንቅናቄዎች ሁሉ ልል ነው። በአባላቱ መካከል የስትራቴጂ፣ የታክቲክ እና አንዳንዴም የአይዲዮሎጂ ልዩነት ይታያል። ለምሳሌ፦ አንዳንዶቹ ሌማት ጠያቂዎች (maximalist) ሲኾኑ ሌሎቹ ደግሞ ኩርማን ጠያቂዎች (minimalist) ናቸው። በርካታ አባላት ጥያቄው ከሕገ መንግሥት እና ከአጠቃላይ የሰብአዊ መብት ጽንሰ ሐሳብ ጋር ብቻ የተገናኘ ዓለማዊ (secular) እንዲኾን ይፈልጋሉ። አንዳንዶቹ ደግሞ ንቅናቄው ሃይማኖታዊነቱን እንዲያስረግጥ ይሻሉ። ጥቂት የማይባሉ አባላት ደግሞ መንግሥት በሃይማኖት ላይ ያለውን ጣልቃ ገብነት ካቆመ አጨብጭበው ወደ ቤታቸው መመለስ ይፈልጋሉ፤ ከእነርሱ በተቃራኒ አንድ ጥያቄ ሲመለስ ሌላ እየጨመሩ ማኅበራዊ ንቅናቄው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በቀጣይነት መሳተፍ እንዳለበት የሚያምኑ አሉ። ከሌሎች የፖለቲካ እና ማኅበራዊ ንቅናቄዎች ጋር መሥራት በሚፈልጉና በማይፈልጉ መካከል ልዩነት አለ። እንደዚህ ዐይነት የውስጥ ሙግቶች እንደ ድክመት ሳይኾን የማኅበራዊ ንቅናቄ ባሕርያት (features) መታየት አለባቸው። መንግሥት ልዩነቶቹን በመጠቀም ንቅናቄውን ለመከፋፈል ሞክሯል። በዚያ ስላልተሳካለት ቀጥተኛ የጭፍለቃ ርምጃዎችን ወስዷል። ይኹንና በዚህ ሳምንት በአውሮፓ እና በአሜሪካ ያንሰራራው እንቅስቃሴ እንደሚያሳየው ንቅናቄው ቢዳከምም አልከሰመም። ከ1966ቱ አብዮት በኋላ ተፈጥረው ለረጅም ጊዜ የቆዩ ማኅበራዊ ንቅናቄዎችን ታሪክ ስናጠና እጅግ በርካቶቹ በነጻ አውጪ ግንባሮች ጥላ ሥር የተሰበሰቡ ኾነው እናገኛቸዋለን። ድምጻችን ይሰማ ከእነዚህ የተለየ ነው። ድምጻችን ይሰማ ያለ ነጻ አውጪ ግንባሮች እና ፖለቲካ ፓርቲዎች ሞግዚትነት በአንጻራዊ ብቻውን ቆሞ ለረዥም ጊዜ መቆየቱ ልዩ ያደርገዋል።

• Source: ሰባት ኪሎ

The post (የቡና ቁርስ) በዚህ ሳምንት የተማርናቸው ሦስት ነገሮች * ኬንያም ኢትዮጵያም ሽብርተኝነት ላይ ሚዛን ስተዋል * ዶናልድ ሌቪን የኔታ ናቸው * ድምጻችን ይሰማ ብርቱ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

ደርባን ደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያዊያን ተገደሉ VOA

$
0
0

south africa

በደቡብ አፍሪካይቱ ደርባን ከተማ ካለፈው ሣምንት ማብቂያ ጀምሮ በውጭ ሀገር ዜጎች ላይ በደረሱ ጥቃቶች ቢያንስ አምስት ሰው መገደሉን የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ትናንት፤ ማክሰኞ – ሚያዝያ 6 / 2007 ዓ.ም ደርባን ከተማ ጎዳናዎች ላይ ሁከት ተፈጥሯል።

ኢትዮጵያዊያኑን ጨምሮ ደርባን ውስጥ የሚኖሩ አፍሪካዊያን በፍርሃት ቤታቸውን ዘግተው ተቀምጠዋል።

The post ደርባን ደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያዊያን ተገደሉ VOA appeared first on Zehabesha Amharic.

የወያኔ  ዜማ በደቡብ አፍሪካ ተሰማ –ከተማ ዋቅጅራ

$
0
0

Ketemaበደል በደልን ይወልዳል እንጂ አያጠፋውም። ችግር ችግርን ይፈጥረዋል እንጂ አያስወግደውም። በደል ፈጣሪ ከላይ ከተቀመጠ… መከራን አምጪ ስልጣን ላይ ካለ… የምንሰማው እና የምናየው ሁሉ ሰቆቃና ዋይታ ነው። ሰቆቃ እና ዋይታ ግዜውን እየጠበቀ የሚፈነዳ የህዝባችን ፍዳ ከሆነ ሰነባብቷል። ሰቆቃ  ፈጻሚዎች እና ናፋቂዎች አናት ላይ ከተቀመጡ ሰቆቃችን ማብቂያ  የለውም። ለኛ የሃዘን እንባችን ለወያኔ ደግሞ  የመዝናኛው ዜማው የሆነ አሳዛኝ ድርጊት ከወደ ደቡብ አፍሪካ እየተሰማ ነው።

የኢትዮጵያ መከራዋ  በይፋ  ከተበሰረበት ግዜ አንስቶ  ከእለት ወደ  እለት ህዝባችን ከሚወዳት አገሩ ሳይወድ በግዱ ተሰዳጅ እየሆነ  ነው። እግዚአብሔር የተፈጥሮ  ጸጋውን አልብሶን እንኳን ለራሳችን ለአለም የሚተርፍ ሃብት በጉያችን ይዘን እንደ  ርሃብተኛ እንሰደዳለን። በልጆቿ የዳበረ እውቀት በልጆቿ የፈረጠመ  ጉልበት በተፈጥሮዎአ ላይ የሚዘምቱ ኃያል ልጆች ኖሮን ሰርተንና በልጽገን አለምን የሚያስደምም እውቀትና ተፈጥሮ ኖሮን ሳለ ገዳይ ነግሶብን አንባ ገነን ተሾሞብን በየአለማቱ ተበተንን። የወገኖቻችንን  ሰቆቃ  በተቃጠለ  ስሜት የደም እንባ እናነባለን። ከአጋም ጋር የተጠጋ  ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል እንደሚባለው ወያኔ ለሆዱ፣ ለስልጣኑ፣ ብሎ ህዝባችን ላይ የሚያደርሰው ግፍና  በደል ህዝባችንን ተሰዳጅ አደረገው። ዛሬ በስደት ላይ ያሉ ወገኖቻችን ለሚደርስባቸው ዘግናኝ ድርጊት ተጠያቂው ወያኔ  ነው።

ከጥቂት ግዜ በፊት የኢትዮጵያ መንግስት ከሳውዲ መንግስ ጋር ከአርባ አምስት ሺህ በላይ የሰራተኛ ግብይት ተፈራርሞ ነበረ። ፊርማው ሳይደርቅ የሳውዲ መንግስ በዜጎቻችን ላይ የሰራውን አሳፋሪ እና  ዘግናኝ በደል እርጉዝ ሴት እህቶቻችን ለብዙ በመድፈር ለሞት ሲዳርጉ በአደባባይ በስለት ሲታረዱ የኢትዮጵያ መንግስት የወሰደው እርምጃ አለመኖሩ ስናይ በደላችን የተዳፈነ  ፍም ሆኖ በውስጣችን ተቀምጧል። ሌላው ቀርቶ በሳውዲ አረብያ በዜጎቻችን ላይ የሚደርሰውን በደል ለመቃወም በአዲስ አበባ ሳውዲ ኤምባሲ ሰልፍ በመውጣት ብሶቱን ለማሰማት የወጣውን ህዝብ የወያኔ ቅልብ ፌደራል በድፍን አምሮው በያዘው በድፍን ዱላ ህዘባችን እየቀጠቀጠ ሳውዲ የወሰደችው እርምጃ  ትክክል ነው ብሎ ነግረውናል።

በመቀጠል በየመን ከ200 ሺህ ሕዝብ በላይ ኢትዮጵያን ይኖራሉ በየመን በተነሳው ግጭት ሳብያ ኢትዮጵያኑ እንደቅጠል እየረገፉ ነው በዚህ መሃል ቀልደኛው መንግስታችን በዚህ ስልክ ቁጥር ደውሉ አልነሳ ካላቹህ መልሳቹህ መልሳቹህ ሞክሩት አልያም መልክት አስቀምጡ የሚል በፌስ ቡክ መስኮት ብቅ ብሎ ነግሮናል። ለየመን ባላሀብት ሲጋራ ሞኖፖልን ከምትሸጡ ይልቅ ለሳዊዲ ባለሃብት፣ ለህንድ እንዲሁም ለገብረመድህን፣ ለኪሮስ፣ ለግደይ፣ ለአላሙዲ፣ የአገሪቱን ለም መሬት ከምትቸበችቡ በችግር ላይ ላለው ዜጋ ለሆኑ አገራቸውን እያለሙ እራሳቸውን እንዲችሉ የአገር ለውጥ በአገር ልጅ የሚለውን   መርሆ  ብትከተሉ  ምን  አለበት? ለነገሩ የሰይጣን መልእክተኛ  አልያም በውስጡ ሰይጣናዊ ሃሳብ ያለበት ይሄን ማድረግ አይቻለውም።

ችግር ፈጣሪው እስካለ  ችግሩ አይቀሬ ነው ።  እናም በሱዳን በኬንያ በዛንብያ በግብጽ ችግሮች እንዳሉ ቢታወቅም እንደ  እሳተ ጎመራ የፈነዳው አዲስ ክስተት በደቡብ አፍሪካ ተከሰተ፡ ትናንት በችግራቸው ጊዜ  ችግራቸውን የሸፈንላቸው ሁሉ ዛሬ እነሱ በኛ ላይ ተነሱ። ሳውዲን ብንወስድ ቆሬሾች ሊገሏቸው ሲያሷድዷቸው የነብዪ መሀመድ ወገኖችን  በጉያዋ ያስቀመጠች  በኔ የተከለሉትን በራሳቸው ፍቃድ ካልሆነ ለማንም  አንባገነን አሳልፌ  አልሰጥም ብላ ህይወታቸውን የታደገች አገር….  ለደቡብ አፍሪካም  የነጻነት መሪ የተባለውን ማንዴላን ተቀብላ አሰልጥና የኢትዮጵያን ፓስፖርት ሰጥታ በክብር የሸኝች አገር ዛሬ ያሁሉ ተረሳና የስቃይ ጅራፍ ውለታ ለዋለችላቸው አገር ሲያደርጉ ያሳዝናል። ታሪክ ይውቀሳቸው እውነት ይፋረዳቸው።

ደቡብ አፍሪካዎች ምን ነካቸው? የማንዴላ ህዝቦች ምን አጋጥሟቸው ነው? እንደዚ ወደ አውሬነት የተለወጡት። እግዚአብሔር ብድራትን ይመልስላቸው በሰይፍ ያጠፋ በሰይፍ ይጠፋል ይላል። ፍርዱን ለፈጣሪ በመተው ከኛ የሚጠበቅብንን ማድረግ ግድ ይለናል።

ነገሮች ሲወጣጠሩ ማስተንፈሻ በመፈለግ ወደ ሰባራ ተግባር የሚሄደው የወያኔ መንግስት ሁሉም ህብረተሰቡ ትኩረት አድርገው ስለ አገራቸው በሚያስቡበት እና በሚሰሩበት ግዜ  በደቡብ አፍሪካ  እንደዚህ አይነቱ ክስተት መከሰቱ ለወያኔ ዜማው ነው። የወያኔ መንግስት ሃሳባቸው ስለ ኢትዮጵያ ህዝብ ሳይሆን ስለስልጣናቸው ብቻ የሚያስቡ በመሆኑ የህዝብ በደል ወይም እልቂት ያስደስታቸዋል ምክንያቱም የፖለቲካ አቅጣጫውን ስለሚጠመዝዝላቸው። ለደቡብ አፍሪካ ጭፍጨፋ የአፍሪካ መሪዎች በዜጎቻቸው እየደረሰ ያለውን  ግፍ ለደቡብ አፍሪካ መንግስት ማስጠንቀቂያ ሲሰጡ ..በጦርነት እየታመሰች ያለችው ሱማሊያ ስለዜጎቿ ስትቆም… ወያኔዎች ግን ምንም ያሉት የለም። በርግጥ ከወያኔ ምንም አንጠብቅም። ምክንያቱም አይተናቸዋልም አውቀናቸዋልም። የሚጠበቀው ከኛው ነው።  እኛው ለኛው።

የህዝባችን እሮሮ ማስቆም የሚቻለው በመጀመሪያ  እሮሮ አምጪውን አናታች ላይ የተቀመጠውን ጨቋኝ አገዛዝ  አውርደን መጣል ስንችል ከዛ በኋላ ዜጋዬ ተበደለ ብለን ስለህዝባችን ፈጥነን መድነስ የምንችለው። ወያኔ ስልጣን ላይ እስካለ ድረስ በህዝባችን ላይ መከራ ቢደርስበት ግድ የለውም። ካሁን በኋላ ወያኔ ህዝባችንን እንዲታደግልን አንጠይቀውም። ለህዝባችን የቆመ መንግስት ነው ብሎም መቀበል አይቻልም። ነገር ግን በህዝባችን ስም በመነገድ ስልጣኑን የሚያራዝመውን ተግባር በማክሸፍ ህዝባችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ እናስቁም። ለዚህም ግዜ የሚሰጠው ጉዳይ አይደለም። በሳውዲ በደረሰው የህዝባችን ሰቆቃ  ምንም ያልፈየደው ወያኔ ሙሉውን ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት ተሸፍኖ ከሳውዲ እንዲመጡ አድርገናል። ከሳውዲ ለመጡት መቋቋሚያ የሚሆናቸውን ገንዘብ እንረዳለን ብለው በአደባባይ የዋሸን መንግስት….. በየመን በደረሰው የወገናችን መከራ የሁሉም አገር መንግስት አውሮፕላን፣ መርከብ በመላክ ህዝባቸውን ሲታደጉ የኛው መንግስት ተብዬው ግን የስልክ ቁጥር ፌስብክ ላይ በመለጠፍ ህዝባችን ላይ የሚያሾፍ መንግስት ተብዬ…. ዛሬ ደግሞ በደቡብ አፍሪካ በህዝባችን ላይ በሚደርሰው ግፍ ሊነግሩን የሚፈልጉት ፌዝ እንዳለ  እናውቃለን። የኛ ውሳኔ ግን ፌዘኛን መስማት ሳይሆን ፌዜኞችን በማስወገድ ለህዝብ የቆመ መንግስት እንዲኖረን ማድረግ ተገቢ ነው።

ከተማ ዋቅጅራ

16.04.2015

Emeil- waqjirak@yahoo.com

The post የወያኔ  ዜማ በደቡብ አፍሪካ ተሰማ – ከተማ ዋቅጅራ appeared first on Zehabesha Amharic.

የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ አመራር ምክር ቤት የተሳካ ጉባኤ አካሄደ

$
0
0

shengoበቅርቡ የሽንጎው ከፍተኛ አመራር አካል የሆነው ምክር ቤት ባካሄደው የሁለት ቀን ስብሰባ  ሀገራችን ኢትዮጵያ የምትገኝበትን ሁኔታ በሰፊው መርምሮ  ለቀጣዩም ትግል ምን መደረግ እንዳለበት መመሪያ በመሰጠት ተጠናቋል።

በተጨማሪም የሽንጎው የተለያዩ የስራ ክፍሎች የስራ አፈጻጸምን በተመለከተ የቀረቡለትን ሪፖርቶች መርምሮ ትግሉ ተጠናክሮ የሚቀጥልበትን ተጨማሪ መመሪያ በመስጠት ተጠናቋል። በተለይም ደግሞ ሽንጎው በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚያካሂደው ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ የተገኙትን መልካም ግንኙነተቶችን እና አበረታች ውጤቶች ከመረመረ በኋላ በዚህ መስክ የሚካሄደው እንቅስቃሴ እጅግ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መመሪያ ሰጥቷል፡

የሸንጎው ምክር ቤት የኢትዮጵያን አጠቃላይ ተጨባጭ ሁኔታ የገመገመ ሲሆን፣ በሀገሪቱ ውስጥ እጅግ ተጠናከሮ የቀጠለውን ሁለንተናዊ የመብት ረገጣ ፣ በተለይም ደግሞ ባሁኑ ሰአት ዜጎች መሰረታዊ የሆነውን መሪዎቻቸውን በድምጻቸው በነጻነት የመመምረጥ መብታቸውን በትክክል እንዳይገልጹ ገዥው ሕወሀት/ኢህአዴግ እና እንደልቡ የሚያዛቸው የምርጫ የጸጥታና የፍትህ ተቋማት በህዝባችን ላይ በቀጣይነት እያሳዩት ያለውን እጅግ አሳዛኛ ግፍ ባፅጽንኦና በታላቅ ሀዘን ተገንዛቧል።

በዚህ እጅግ ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ፣ የፖለቲካ መድረኩን ለገዥው ቡድን ባለመተው የህዝባችንን መብት ለማስከበር እጅግ ብዙ መስዋእትነት ለከፈሉ እና በመክፈል ላይ ለሚገኙ ታጋዮች ሁሉ ያለውን አድናቆት አክብሮትና የትግል አንድነት ምክር ቤቱ በድጋሜ አረጋግጧል።

ገዥው ቡድን ሕወሀት ኢህአዴግ የህዝባችንን መብት በሁሉም መልኩ መርገጡን በቀጠለ ቁጥር ህዝባችን ደግሞ በስርአቱ ላይ ያለው ብሶት ቅሬታና  ጥላቻ፣ እጅግ እየሰፋ መምጣቱን፣ የሚደርስበት ግፍ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ እንደሆነም ብዙ መረጃወችን ምክር ቤቱ ተመልክቷል።ዛሬ ህዝባችን ከዚህ ስርአት መልካም ነገርን መጠበቅ ትቷል፡ በራሱ አነሳሽነት ስርአቱ እንዲወገድለት አምርሮ ይፈልጋል፡ አልገዛም ማለትን በየቦታው እያሳየ ነው። ለመብቱ መቆምን፣ በግልጽ ማሳየቱን ቀጥሏል፤ የፍርሀት ድባብን አፈራርሶ በመጣል ላይ ይገኛል።

ከዚህ በተጨማሪም በገዥው ሕወሀት ኢህአዴግ ውስጥ የርስበርስ አለመተማመን እና ውጥረትም እየሰፋ መምጣቱን የሽንጎው ከፍተኛ አመራር  ምክር ቤት በሰፊው ቃኝቷል።

እነዚህን ሁሉ ባንድ ላይ ስንመለከትም ሀገሪቱ ውስጥ ህዝባዊ የለውጥ አመጽ ሊነሳ የሚችልበት ሁኔታ እጅግ በፍጥነት እየተቃረበ መሆኑን ሽንጎው ተገንዝቧል።

ገዥው ሕወሀት ኢህአዴግ ከላይ  ሲታይ ሁኔታወችን የተቆጣጠረና የተረጋጋ ይምሰል እንጂ ከሁሉም ህዝብ፣ ከሁሉም ፖለቲካ ድርጅቶች፣ ሲቪክ ማህበራት የሀይማኖት ተቓሞች ጋር የገባበት ቅራኔ የራሱን ጥላ ሳይቀር ማንንም እንዳያምን ስላደረገው እነሆ ሌትም ቀንም በመደናበር ካንዱ ስህተት ወደሌላው እየተላተመ ወደ መጨረሻው መቃብሩ እንደተቃረበ እንረዳለን።

ሀላፊነት የጎደለው ሕወሀት ኢህአዴግ ጠባብ ቡድን ከራሱ ስልጣን እና አልጠግብ ባይ ዝርፊያ ባሻገር ለማገናዘብ ባለመቻሉም ሀገሪቱን ራሷን ወደ አደጋ አፋፍ አድርሷታል።

ይህን ሀገራችን የምትገኝበትን ሁኔታ የሚከታተሉ የሀገሪቱ ጠላቶችም የህዝባችንን የለውጥ እንቅስቃሴ ለአደጋና ለራሳቸው ቀጣይ አጥፊ አጀንዳ ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ ሸንጎ ተገንዝቧል።

ሐገራችንና ህዝባችን ከታሰሩበት  የግፍ ሰንሰለት ነጻ ለማውጣትና በምትኩም  አንድነቷ በተጠበቀ ኢትዮጳያ ስር ህገመንግስታዊ ዴሞክራሲአዊ ስርአትን ለመገንባት የሚደረገው ትግል ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሽንጎው ምክር ቤት መመሪያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህን ትግል ወደግብ ለማድረስም ሆነ ከላይ የጠቀስናቸውን አሳሳቢ ሁኔታወች ለማስወገድም ያንድነት ሀይሎች ከምን ጊዜውም በላይ በመተባበር በንቃት እንዲንቀሳቀሱ ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።

ሐገራችን ከምትገኝበት አስከፊ ሁኔታ ሁሉም አሽናፊና ተጠቃሚ ወደሆነበት ስርአት ለመሽጋገር ብሄራዊ መግባባትና ብሄራዊ እርቅ አማራጭ የሌለው እንደሆነ ምክርቤቱ አጽንኦ ሰጥቷል።

የሸንጎው ያመራር ምክር ቤት ዛሬ በሚካሄደው ትግል ውስጥ ያማራጭ ሚዲያን አስፈልጊነት በሰፊው ከተወያየ በኋላ፤ ወደ ኢትዮጵያ የሚተላለፍ ያጭር ሞገድ ሬዲዮ ፕሮግራም ባስቸኳይ እንደሚያስፈልግና፣ ይህን እቅድ ተግባራዊ ለማድረግም በውጭ የሚገኙ እትዮጵያውያን በገንዘብ እና ጊዜያቸውን በማበርከት ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

The post የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ አመራር ምክር ቤት የተሳካ ጉባኤ አካሄደ appeared first on Zehabesha Amharic.

በደቡብ አፍሪካ እየተፈጸመ ያለውን ስደተኞችን የማጥቃትና ማሳድድ ወንጀል በመቃወም ሰልፈኞች ድምጻቸውን ሲያሰሙ ዋሉ

$
0
0

south africa
ኢሳት ዜና :- በደቡብ አፍሪካ የውጪ ሀገር ዜጎች ላይ የተፈጸመው ጥቃት ያስቆጣቸው በርካታ ደቡብ አፍሪካውያን ደርጊቱን ለማውገዝ በደርባን ታላቅ ሰልፍ ማድረጋቸውን የአገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ደቡብ አፍሪካውያን እና የውጭ አገር ዜጎች በሰልፉ ላይ ተገኝተዋል። “የውጪ ሀገር ዜጎችን ማጥቃትና ማሳድድ ይቁም!” የሚል መፈክር ያነገቡት የደርባን ነዋሪዎች፤ በጥቃት ፈጻሚዎቹ ላይ ተቃውሟቸውንና ቁጣቸውን ገልጸዋል።

ሰልፈኞቹ ትናንት በደርባን የተፈጸመውን ድርጊት ከማውገዝ ባሻገር ለውጪ ሀገር ዜጎች ያላቸውን አጋርነት በይፋ አረጋግጠዋል።.
ሰሞኑን በደርባን በተፈጸመው ጥቃት በትንሹ 5 ሰዎች መገደላቸውንና የበርካታ ሰዎች ሱቆች መዘረፋቸውን ቢቢሲ አመልክቷል። ከሟቾቹ ውስጥ ሶስቱ ኢትዮጵያውያን ናቸው።

በደርባን የሚገኙ ኢትዮጵያኖች ራሳቸውን ከጥቃት ለመከላከል አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰዱ ነው። በደቡብ አፍሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ወኪል ወደ ደርባን በማቅናት ኢትዮጵያውያኑን ማነጋገሩን የደሰረን መረጃ ያመለክታል። ኢትዮጵያውያን በወገኖቻቸው ላይ የደረሰውን ጥቃት የማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃንን በመጠቀም እያወገዙት ነው።

በደርባን የተፈጸመው እርምጃ በጆሃንስበርግም ይደገማል የሚል የስልክ መልእክት ተላልፎአል በሚል፣ በከተማዋ የሚገኙ የውጭ አገር ነዋሪዎች ሱቆች ተዘግተው አርፍደዋል።

እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2008 ዓመተ ምህረት በውጪ ሀገር ዜጎች ላይ በተፈጸመ ተመሳሳይ ጥቃት 62 ሰዎች እንደተገደሉ መዘገብቡ አይዘነጋም።

የዙሉ ንጉስ የውጪ ሀገር ሰዎች ሻንጣቸውን ሸክፈው ወደሀገራቸው መሄድ አለባቸው በማለት ያደረጉት ንግግር ለጥቃቱ መጀመርና መባባስ ዋነኛ ምክንያት መሆኑ ተመልክቷል። እርሳቸው ግን ለችግሩ ተጠያቂ አይደለሁም በማለት አስተባብለዋል።
ጥቃቱ መፈጸሙን ተከትሎ ማላዊ ዜጎቿን ከደቡብ አፍሪካ በማውጣት ቀዳሚዋ ሀገር ስትሆን፤ ዚምባቡዌም ድርጊቱን በይፋ በማውገዝ በውጪ ዜጎች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እንዲቆም ጠይቃለች።

The post በደቡብ አፍሪካ እየተፈጸመ ያለውን ስደተኞችን የማጥቃትና ማሳድድ ወንጀል በመቃወም ሰልፈኞች ድምጻቸውን ሲያሰሙ ዋሉ appeared first on Zehabesha Amharic.

ከአረብ ሀገር እስከ ደቡብ አፍሪካ * የስደተኛው ሮሮና የመንግስት ቸልተኝነት ! (ይድረስ ለክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም …)

$
0
0

ነብዩ ሲራክ ከሳዑዲ አረቢያ

የማለዳ ወግ …ከአረብ ሀገር እስከ ደቡብ አፍሪካ
የስደተኛው ሮሮና የመንግስት ቸልተኝነት !

* ይድረስ ለክቡር ዶር ቴዎድሮስ አድሃኖም …
* ኢህአዴግን እንዴት እንምረጥ ?

ትናንት በሁከት ፣ ዛሬ በመፈራረስ በሚመስል አደገኛ የለውጥ ሂደት ውስጥ ባለችው የመን የኢትዮጵያውያን የድረሱልኝ ድምጽ ከነኡኡታው ሰላም ይነሳል ። በደቡብ አፍሪካ በኢትዮጵያውያን ስደተኛ ወገኖቻችን ላይ ከኢራቅና ሶርያ አይ ኤስ አይ ኤስ ISIS ጽንፈኞች ባላነሰ ከፍ ሲል በሰብአዊው ዜጋ ፣ ዝቅ ሲል ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በተለያዩ የውጭ ዜጎች ላይ የተጀመረው ጥቃት ሊያዩት ሊሰሙት ይከብዳል ። በሰላ ገጀራ ፣ ሰንጢ የሰው ፍጡር የመቆራረጥና ፣ በእሳት የማቃጠልን የአውሬ ተግባርን መመልከት ዘልቆ ልብን ይሰብራል ። ይህ ሁሉ ሲሆን ” መንግስ አለን !” ባዮች ኢትዮጵያውያን ፈጥኖ ደራሽ ቀርቶ ጉዳቱን አጥብቆ የተቃወመ መንግስት ባለማየታችን አዝነናል !
Saudicry
በአንድ ወቅት ብቻ ሳይሆን በተደጋጋሚ ” ኢህአዴግን ምረጡ !” በሚል በማህበራዊ መገናኛ የፊስ ቡክ ቅስቀሳ ዘመቻዎ ባስተላለፉት መልዕክት የፈረደበት መንገድ ፣ ህንጻውንና ግድቡን በፎቶ አሸብርቀው ” እነሆ ሰርተን አሳይተናል ፣ ስራ ላይ ነን !” በማለት “የወሬ የለው ፍሬ ” በሚልና “ስራ እንጅ ወሬ አናውቅም ” የሚል አንድምታ ያለው መልዕክት አስተላልፈው ተመልክቻለሁ ። ለድርጅትዎ ቀናኤ መሆንዎን አልቃወምም ። ዳሩ ግን በስደት ህይዎቴ በድርጅትዎ የሚወከሉ ባለስልጣኖችም ሆኑ ተራ የድርጅትዎ ካድሬዎች የመንገድ ህንጻውንና ግድቡ ከእነ ተሳላጠው የሃገር እድገት እያነሱ በመጣል ከመደስኮር ፣ ለድጋፍ ገንዘብ ለመሰብሰብ ከሚደረገው ድግስና የስብሰባ ጥሪ ባሻገር ለዜጋው መብት ማስከበር ቆመው አይቸ ፣ ሰምቸ አላውቅም ። እናም ሀገር የማለት ትርጉሙ ቅጥ አንባሩ ይጠፋብኛል !

በማዲባ ምድር በደቡብ አፍሪካ በዜጎች ላይ እየተፈመ ያለውን አሰቃቂ ግፍ እንደ ዜጋ አሞኛል ። ድርጊቱን በአደባባይ የሚያወግዝልን መንግስት ማጣታችን አውጥቸ አውርጀ ለዜጎች መብት ማስጠበቅ ተግቶ የማላውቀው ኢህአዴግን ብመርጥ ሀገሬ ህዝቤ ምን እንደሚሆኑ ማሰቡ አልተሳነኝም ። …አናም መንግስትዎ እንደ ዜጋ የስደተኛ መብታችን ካስጠበቀልን እንጅ ግዑዙን መንገድ ስለሰራ ፣ ህንጻውን ስላቆመና ግድቡ ስለገደበልኝ ፣ በአንጻሩ መሆን አለበትን ? ስል ከራሴ የወጣ ፈታኝ ጥያቄ አንገላታኝ… እናም ትናንትም ሆነ ዛሬ ኢህአዴግ ለዜጎች መብት እስካልተጋ ድረስ እንዴት ኢህአዴግን እንምረጠው ? አልኩ ቢቸግረኝ …

የሆነው እና እየሆነ ያለው ቢያከፋኝና ፣ ቢያስጨንቅ ፣ ቢያስጠብበኝ ወቀሳ ቢጢ ልልክልዎ ነሸጠኝ … ! ብዕሩን በቀለም ነከሬና ወረቀቱን አቅርቤ የታወከው ውስጤ እርሙን ያወጣ ዘንድ እንደለመድኩት በማለዳ ወጌ ብሶቴን መተንፈሱን መረጥኩ … ንዴት ብስጭቴ አይሏልና ክብርዎን እንዳልነካ በመጠንቀቅ እራሴን አረጋግቸ ስሞታ ፣ ቅያሞቴን አሳምሬ በማውቀው የአረብ ሀገሩ ስደት በጨረፍታ ልጀምረው ፈቀድኩ … !

ከሁሉ በማስቀደም ከ20 ዓመታት ወዲህ ዘንድሮ ወግ ደርሶን ባለሙያ ወደ አካባቢው መላኩን ባልክድም ፣ ከዚህ ቀደም በአረብ ሃገራት በዜጎች መብት ጥበቃ የገጠመን የባለሙያ ተወካይና የመንግስት ትኩረት እጦት ፈተና ግን እንዲህ በአጭሩ የሚገለጽ አለመሆኑን ከጅመሩ አስረግጨ ልነግርዎ ደስ ይለኛል ! …ግን በአጭሩ ልሞክረው …

እርስዎ የጤና ጥበቃ ሃላፊ ከመሆንዎ በፊት ጀምሮ እስከዚህች ሰዓት ላለፉት 20 አመታት በአረብ ሀገር የመ ብት አስጠባቂ ተቆርቋሪ አጥተን ስለመናቅ መዋረዳችን ፣ ስለመገፋት መገደላችን ፣ ስለ ስደቱ አስከፊነት የሚደ ርሰውን በደል በከፊልም ቢሆን በማቀርባቸው መጣጥፎች ባለፈ በአንጋፋው የጀርመን ራዲዮ የዜጎችን ይዞታ ላልሰሜ ለማሰማት ሞክሬያለሁና ” ሁሉን ቢባገሩት ሆድ ባዶ ይቀራ ል ” የምል ዜጋ አይደለሁም ! እኔን ሆንኩ መሰሎቸ የዜጎች መብት ይከበር ፣ የመብት ጥበቃ ይደረግልን እያልን ድምጻ ችን ያሰማን ቢሆንም ሰሚ በማጣታችን ግፉ ከጠበቅነው በላይ ሆኖ አሁን ድረስ ቀጥሏል …

የእኛ እውነት የእናንተ ስህተት …
====================

ክቡር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር …
እርስዎ የተኳቸው የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና የአሁኑ የተከበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ወደ ሳውዲ አረቢያ ለጉብኝት መጥተው የኮንትራት ስራ ኢትዮጵያውያንን ለመቀበል ሳውዲዎች ፍላጎት ማሳየታቸ ውን ለሳውዲ ታዋቂ ጋዜጦች መግለጫ ሰጥተው እንደ ሄዱ ያለምንም ቅድመ ዝግጅትና ጥናት የኮንትራት ስራውን ሲጀመር ከቀሩት ወገኖቸ ጋር በመሆን ህጋዊ የኮንትራት የሁለትዮሽ ውል ሳይደረግ ዜጎችን መላኩ አደጋ አለው በሚል የተቃውሞ ድምጻችን ስናሰማ የስምምነት ህጋዊ ውሉን መፈራረምና አማራጩ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ነው ብንልም ሰሚ አላገኘንም ። በአጭር ጊዜ ህጋዊ ውል በሌለው ስምምነት በኮንትራት ስራ ስም ዜጎች ይላኩ ጀመር ። ከጅምሩ እስከ አሁን ያለውን አሰቃቂ የእህቶቻችን የመከራ ዋይታ መስማት ጀመርን ። እርስዎ ወደ ስልጣን በመጡ ማግስት ያለምንም ጥናትና ቅድመ ዝግጅት የተጀመረውን በድርጊቱ ሁሉ ከታመሙት መካከል የምወዳት ሃገሬ እጓለማውታ ስደተኛ አንዱ እኔ ነኝ !
Tedros-Adhanom-
ምንም እንኳን ዛሬ መንግስትዎ ዜጎችን ያለ ሁለትዮሽ ውል ወደ አረብ ሀገራት ለስራ መላኩ ስህተት እንደነበር ማመኑን ሳስበው እታመማለሁ። ዛሬ እውነቱ በሂደት ፍን ትው ብሎ ወጥቶ እኛ የሰጠነው መረጃ ትክክል እናንተ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በኮንትራት ስራ ስም ያለ ውል መላካ ችሁ ስህተት መሆኑን ብታምኑም የዜጎች ህይዎት የተገበረበት የአካሄድ ስህተት አንኳ ይቅርታ አልጠየቃችሁም። ይባስ ብላችሁ አሁንም ባለ ድርሻ አካላት በግልጽ ያልመከሩበት አዲስ ህግ ተረቆ ለትግበራ ጥድፊያ ላይ መሆናችሁ ለዜጎች ታስቦ ነው አልልም ። ያኔ እንደ ዜጋ አግብቶን ስንናገር ባለመሰማታችን እናንተ ተሳሳታችሁ እነደነበር ዛሬ በአደባባይ አመናችሁ ፣ ዛሬም እንደ ዜጋ አግብቶን ረቂቅ ህጉን ባለድርሻ ዜጎች ይወያ ዩበት ስንል ሰሚ አጥተን ” ግመሏ ትሄዳለች ውሻዎች ይጮሃሉ! ” አይነት የተለመዴ አካሄድ የተያዘ ለመሆኑ የሚያሳብቁ ኩነቶች ታጅበን እየተጓዝን እንገኛለን ! ከአንድ አመት በፊት ” ስደት ይብቃ !” በሚል መሪ ቃል በሚሊኒየ ም አዳራሽ ከአፍ እስከ ደገፉ የሞሉ ታዋቂ ሰዎችና ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎች ልብ አሸብሮ ያስለቀሰው ግፍ እንዲፈጸም ምክንያቱ ስህተታችሁ አልነበረምን? ዛሬስ እንዴት ያ ሁኔታ ባለበት እንዲቀጥል ትፈቅዳላችሁ ? ለምንስ አትሰሙም ?

በደቡብ አፍሪካስ ለኢትዮጵያውያን የት አላችሁ?
==============================
ክቡር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶር ቴዎድሮስ…

ወገን በደቡብ አፍሪካ ለሳምንት በአጣብቂኝ ውስጥ ወድቆ ከአይሲኤስ በማይተናነሱ የደቡብ አፍሪካ አውሬዎ ች በኢትዮጵያውያን ላይ ግፍ ሲፈጽሙ የት አላችሁ ? ኢት ዮጵያውያን ስደተኞች ሃብት ንብረታቸውን እየተቀሙ ፣ እየተ ዘረፉ ሲሳደዱ ፣ ሲወገሩ ፣ በእሳት ሲነዱንና ጨፈጨፉ ሲፈጸምባቸው ማትረፍ ባትችሉም እንዴት ድርጊቱን ማውገ ዝ ተሳናችሁ ? ዜጎች መደፈር የአገር ህመም አልሆን ብሎ ፣ የሀገራቱ ሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊው ግንኙነት እንዳይ ናጋ ይሆን ? እውነት እልዎታለሁ … እርስዎ በከፍተኛ ኃላ ፊነት ያስቀመጠዎ መንግስት ፣ እርስዎም እንደ ውጭ ጉዳይ ኃላፊነትዎና እንደ ዜጋ የዜጎችን መብት ለማስከበር ተቃውሞ ድመወጻችሁን ለአለም አላሰማችሁም ። ይህም ስታደርጉ ትልቁን ሃላፊነት አልተወጣችሁምና አዝኛለሁ !
south africa
ከአፖርታይድ የነጻነት እለህ አስጨራሽ ትግል በደ ገፍናት ፣ ለመሪዋ ለማንዴካ መሸሸጊያ ፣ ለታጋይ ፋኖዎቿ መጠጊያና ስንቅ ትጥቅ ያቀበለችው ሃገር ዜጎች በደቡብ አፍሪካ ዘረኛ ወሮበሎች ተደፍረናል ። በህግና በስርአት በምትመራ በምትባለው ስልጡን አፍሪካዊት ሀገር በደቡብ አፍሪካ ፣ በአለማችን የነጻነት ታጋይ በክቡር ኔልሰን ማን ዴላ ምድር ፣ ነጻነቷን ከወራሪ አስከብራ የኖረችው ሀገር የኢትዮጵያ ልጆች ግፍ ተፈጽሞብናል ። በዘር ጥላቻ የወገን ደም ረክሶ በሰላ ገጀራ አካላቸው ሲጎመድ ፣ ሲቃጠሉን ሲገደሉ እያያችሁ ዝምታን መምረጣችሁ እኔ በግል በመን ግስት ላይ ተስፋ እንድንቆርጥ አድርጎኛል ። አፋጣኝ የወ ገን አለኝታነትን አለማሳየታችሁ እኔን ብቻ ሳይሆን ሀገር ወዳዱን ደጋፊዎችዎን ሁሉ ማስቆጣቱን ማምሻውን በለቀ ቁት ብጣሽ መረጃ ስር የተጻፈውን የሰላ ሂስ ማንበቡ ብቻ በቂ ይመስለኛል ።

ክቡር ሚኒስትር ዶር ቴዎድሮስ በደቡብ አፍሪካ ዜጎ ቻችን ላይ አፋጣኝ እርምጃ አለመውሰዳችሁ በመስሪያ ቤትዎም ሆነ በመንግስት ተስፋ ያልቆራጥን የነበርንን ጥቂት ገለልተኛ ነን የምንል ወገኖችን ሞራል አልጠበቀል ንም ። ከእኛ አልፎ ሲደግፉ ያው ግዑዙን መንገድ ህን ጻውን ፣ ግድቡን ፣ “ተንፈላሰሳችሁበት ” የሚሉንን ሞክ ራሲና እድገቱን ከመጥቀስ ፈቀቅ የማይሉ ፣ የሚሰደደውን ህልቀ መሳፍርት ዜጋ ድህነት ፣ የኑሮ ውድነትና የአውራ ፖርቲ ፖለቲካ ትንኮሳ ምክንያት አስረግጠው ለማስረዳት በቂ ምክንያት የሚያጥራቸውን ከነፍሳቸው ጋር የታረቁ ደጋፊዎቻችሁን ተቀይመዋችኋል። እነሱን ለማጽናናት ሲባል ቢያንስ
” … የኢህድሬ መንግስት ና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዜጎቹ የሚፈጸመውን አሰቃ ቂ በደል በመቃዎም የደቡብ አፍሪካን አንባሳደር በአስቸኳ ይ ጠርቶ አፋጣኝ እርምጃ እንዲዎስድ ማስጠንቀቂያ ሰጠ ! ይህ ካልሆነ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት እስከመቋረጥ የሚያደርስ እርም እንደሚወስድ መንግስት ያወጣው መግለጫ አስታወቅ !”
ተብሎ በቴሌቪዥንና በራሳችሁ ራዲዮ መስማቱን ናፍ ቀነው የውሃ ሽታ ሆኖ ሳንሰማው ቀረን … እርስዎም ቢሆን መረጃው እንደ ደረሰዎ በትኩሱ በለመድነው ዘመነኛ መረ ጃ ቅበላዎ የረባ መረጃ ስላልሰጡን የለውጥ ተስፋ ያለን ሁሉ ምኞት ከንቱ መሆኑን አሳይቶ የማይጨበጠውን ተስፋ አጨናግፎታል !

እንደ ከሸፍን እንዳንቀር ፣ ከኢትዮጵያ መንግስት የምንጠብቀው …በጥሞና ይስሙኝ !
==========================

ክቡር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር …
ክቡርነትዎም ሆኑ የሚመለከታችሁ እንዲህ እንደ ተዋረድን ፣ እንደ ከሸፍን እንዳንቀር ፣ በደቡብ አፍሪካ የተፈጸመብንን ግፍ የሚመለከት ከእርስዎና ከኢትዮጵያ መንግስት የምንጠብቀው ከብዙ በጥቂቱ ሃሳቤ የሚከተለው ነውና በጥሞና ስሙኝ !

1ኛ / የኢትዮጵያ መንግስት በደቡብ አፍሪካ እየተፈጸመባቸው ላለው ግፍና በደል ለድርድር እንደማይቀርብ በማስገንዘብ ለአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን በአደባባይ ከዚያም አልፎ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ጠንከር ያለ መግለጫ መስጠት አለበት ።

2ኛ / ለነጻነት ትግሉ ከፍተኛ ተጋድሎ ያደረገችው ሃገር የኢትዮጵያ ዜጎች በደቡብ አፍሪካ የተፈጸመባ ቸውን ግፍ ህዝብን ያስከፋ ያስቆጣ ድርጊት መሆኑን በሀገር ቤት መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር በግልጽ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፎች እንዲደረጉ መፍቀድ ።

3ኛ / ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ ያደረጉትን የደቡብ አፍሪካ ፣ የአፍሪካ ህብረት ፣ የተባበሩት መንግስታትን ከፍተኛ ኃላፊዎች በመጥራት በዜጎቻችን ላይ የተፈጸመው በደል የሁለቱን ሃገር ግንኙነት እስከ ማቋረጥ የሚደርስ እርምጃ እንደሚያስከትል ከበድ ማስጠንቀቂያ መስጠት ።

4ኛ / በህግና ስርአት የፕሬ ጃኮብ ዙማ ትተዳደራለች በምትባለው የደቡብ አፍሪካ መንግስት ግፍ በዜጎቻችን መፈጸሙን በአጽንኦት ለማስረዳት በጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆነ በእርስዎ የሚመራ ቡድን በአስቸኳይ ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊሄድ ይገባል ።

5ኛ / ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ የሚፈልጉ ዜጎች ለጉዳታቸወና ለተዘረፉት ንብረት ካሳ መጠየቅ ።

6ኛ / ወደ ሀገር መመለስ ለሚፈልጉ ተመላሽ ዜጎች አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ ፣ ወደ ሶስተኛ ሀገር መሔድ ለሚፈልጉ መብታቸውን ማክበር ይገባል ።

በደቡብ አፍሪካ ያላችሁ ዜጎች ብርታቱነን ይሰጣችሁ !
የሞቱትን ነፍስ ይማር ከማለት ባለፈ መሄድም ሆነ ክብራች ን መመለስ ባይቻልም ፣ ሀገርና መንግስት አለን ለማለት አፋጣኝ እርምጃ ከመንግስትዎና ከመስሪያ ቤትዎ እንጠብቃለን !

ሀገር ማለት ህዝቡ ነው !

ከሰላምታ ጋር !

አክባሪዎ

ነቢዩ ሲራክ
ሚያዝያ 9 ቀን 2007 ዓም

The post ከአረብ ሀገር እስከ ደቡብ አፍሪካ * የስደተኛው ሮሮና የመንግስት ቸልተኝነት ! (ይድረስ ለክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም …) appeared first on Zehabesha Amharic.


የደቡብ አፍሪካው የስደተኛ ጠልነት መነሻው ምንድነው? (የሰባት ኪሎ ወቅታዊ አጭር ትንተና)

$
0
0

ethiopia south africa
ደቡብ አፍሪካን በቅርቡ የማይከታተሉ ሰዎችን በእጅጉ ያስደነገጠ ቢኾንም በአገሪቱ ስደተኞች ላይ ያነጣጠረ ኹከት ሲካሄድ የአሁኑ የመጀመርያው አይደለም። እ.ኤ.አ በግንቦት ወር 2008 አሌክሳንደር በተባለ የጆሃንስበርግ ታውንሺፕ የተነሳ ኹከት ወደ ደርባን እና ሌሎች ከተሞች ተዛምቶ ቢያንስ ለዐርባ ስደተኞች መሞት ምክንያት ኾኗል። በኹከቱ ብዙ ንብረት ወድሟል። ከዚያ በፊት እና በኋላም ቢኾን ሌሎች በርካታ አነስተኛ ጥፋቶች ተፈጽመዋል። ይህ ለብዙዎች እንቆቅልሽ ነው “በጉርብትና የሚኖሩ ሰላማዊ ስደተኞችን በእንደዚህ ዐይነት ጭካኔ ማቃጠል፣ መግደል እና መደብደብ ለምን?” የሚለው ጥያቄ ተደጋግሞ ይነሳል። በደቡብ አፍሪካ እንዲህ ዐይነት ከፍተኛ የኾነ ስደተኛ ጠልነት ለምን ተስፋፋ የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ምናልባትም ወደ አገሪቱ የመጀመርያዎቹ የዴሞክራሲ ዓመታት መለስ ብሎ መመልከት አስፈላጊ ነው።
gejera south africa

ከኻያ ዓመታት በፊት አፓርታይድ ተገርስሶ ዴሞክራሲያዊ ሥርዐት ሲጀመር በደቡብ አፍሪካ ሁለት ነገሮች ተፈጠሩ። በመጀመርያ ብዙኃኑ ጥቁሮች ከጥቂት ነጮች ጭቆና ተላቀው እነርሱ በመረጡት መንግሥት አስተዳደር አማካኝነት ከነበሩበት የኢኮኖሚ ችግር እንደሚወጡ ተስፋ ሰነቁ። በጊዜው የወጡ የሕዝብ አስተያየት ጥናቶች እንደሚያሳዩት በርካቶች ከነጭ ሀብታሞች ተቀንሶ ለድኾች የሚሠጥበት የኢኮኖሚ መልሶ ማከፋፈል (economic redistribution) ይኖራል የሚል ተስፋ ነበራቸው። ከፍ ያለ የትምህርት ዕድል፣ ቀስ በቀስ የሚያድግ ገቢ፣ የተሻለ የመኖርያ ቤት የማግኘት ፍላጎት ጨመረ። በሌላ በኩል በተለይ በምዕራብ አገሮች መንግሥታት እና ነጭ ደቡብ አፍሪካውያን ዘንድ አዲሱ ዴሞክራሲ የንብረት መብትን ይሸረሽራል፣ የኤኤንሲ መንግሥት ከመራጮች በሚመጣ ጫናም ይኹን በውስጥ ፖለቲካው ምክንያት መልሶ ለማከፋፈል ሲል ንብረት ይወርሳል፣ ከባድ ግብር ይጥላል ወዘተ . . . የሚል ስጋት ነበር።

ይኹንና የድኻ ጥቁሮች ተስፋም ይኹን የሌሎቹ ስጋት እውን አልኾነም። ማርቲን ፕላውት እና ፖል ሆልደን “Who rules South Africa?” በሚል መጽሐፋቸው እንደሚያትቱት ኤኤንሲ ሥልጣን ላይ እንደወጣ ከወሰዳቸው የመጀመርያ ‘ርምጃዎች መካከል አንዱ እ.ኤ.አ በ1955 የነጻነት ቻርተር ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ይዞት የቆየውን ሶሻሊስታዊ ኢኮኖሚ አስተሳሰብ ትቶ በቅይጥ ኢኮኖሚ መተካቱ ነበር። የቅይጥ ኢኮኖሚ ፖሊሲዎቹም ቢኾኑ ብዙም ተግባራዊ ሳይደረጉ ተራግፈዋል። ግራ ዘመም የሚባለው እና በኔልሰን ማንዴላ ይደገፍ የነበረው መልሶ የመገንባት እና የልማት ፕሮግራም (Reconstruction and Development Programme) ለሁለት ዓመታት እንኳን በቅጡ ተግባራዊ ሳይኾን በጊዜው ምክትል ፕሬዝዳንት በነበሩት እና አሁን በተለያዩ የአፍሪካ አገራት እየተዘዋወሩ ‘ኒዮ-ሊበራሊዝምን እቃወማለሁ’ እያሉ በሚናገሩት ታቦ ምቤኪ ውትወታ ወደ ቀኝ ባዘመመው የዕድገት፣ የሥራ እና የመልሶ ማከፋፈል ስትራቴጂ (Growth, Employment and Redistribution Strategy) ተተካ። በመጀመርያው ፕሮግራም ተጀምረው የነበሩ የመኖርያ ቤት አቅርቦት ፕሮጀክቶች፣ ለድኾች የሚሰጡ የተለያዩ ድጎማዎች፣ የመጠጥ ውሃ፣ ንጹሕ የመጻዳጃ ቤቶች እና መብራት ማስፋፋት በሁለተኛው ፕሮግራም እየተዳከሙ መጡ። እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ ለድኻ ደጋፊ ፖሊሲዎች ብዙ ቁብ ያልነበረው የዓለም ባንክ ሳይቀር ይህ የፖሊሲ ለውጥ አስጨንቆት የደቡብ አፍሪካ መንግሥት መጠነኛ ማሻሻያ እንዲያደርግ ምክር ለግሶ ነበር። ኤኤንሲ ሥልጣን ላይ ከወጣ ከዐሥር ዓመታት በኋላ በአገሪቱ የተመዘገበው ኢ-እኩልነት እ.ኤ.አ በ1970ዎቹ እና በ1980ዎቹ በአፓርታይድ ሥርዐት ወቅት ከነበረው ጋር ተስተካከለ። ከዚያም በኋላ ብልጫ አሳየ። የሚገርመው ኢ-እኩልነቱ በፍጥነት የጨመረው የደቡብ አፍሪካ አማካይ ዕድገት አመርቂ ነው በሚባልበት ወቅት ነበር። ድህነት ቀነሰ ቢባልም ፍጥነቱ እጅግ ዝግ ያለ ነበር። በርግጥ ጥቂት ጥቁር ልሂቃን እና ከመንግሥት ጋር ግንኙነት ያላቸው ነጋዴዎች በተለይ የጥቁሮችን የኢኮኖሚ ኃይል ለማሳደግ በወጣው Black Economic Empowerment ፖሊሲ ተጠቅመው የበለጸጉ ቢኾንም ለብዙኃኑ ደቡብ አፍሪካውያን አዲሱ የዴሞክራሲ ሥርዐት ያመጣው የኢኮኖሚ ጥቅም እዚህ ግባ የሚባል አይደለም። በዚህም ምክንያት የብዙዎች ተስፋ ተቀጨ። ቁጣ እና ንዴት ጨመረ፤ ድህነት፣ ሥራ አጥነት እና የአገልግሎት አቅርቦት ችግር ተስፋፋ፣ በየታውንሺፑ በየጊዜው የሚደረጉ ከአገልግሎት አቅርቦት ችግር ጋራ የተገናኙ ዐመጾች ተበራከቱ። ለዚህ እና ለሌሎች ኢኮኖሚ ነክ ዐመጾች መንግሥት የሚሰጠው ምላሽ አንዳንዴ እንዳልተፈጠሩ እና እንዳልነበሩ አድርጎ መርሳት፣ አንዳንዴ ኃይል የተቀላቀለበት ጨካኝ ርምጃ መውሰድ፣ ምርጫ ሲደርስ ደግሞ ሥንዝር ጉቦ እየሰጡ ለማማለል መሞከር ነው። ለምሳሌ፦ እ.ኤ.አ ነሐሴ 2012 የደሞዝ ጭማሪ የጠየቁ በማሪካና አካባቢ በማዕድን ቁፋሮ ላይ የተሰማሩ ጥቁር ሠራተኞች ላይ መንግሥት ተኩስ ከፍቶ 34 አድመኞችን ሲገድል 78 አቁስሏል።
Gejera south africa

ደቡብ አፍሪካ ዴሞክራሲ ስትጀምር ሌላው የተፈጠረ ነገር ወደ አገሪቱ የሚመጡ ስደተኞች ቁጥር (በተለይ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት) በፍጥነት መጨመር ነበር። የኤኤንሲ መሪዎች ቀስተ ደመናዋ አገር (the rainbow nation) የሚል አገሪቱ ብዙ ዘሮች፣ ብሔረሰቦች እና ጎሳዎች በሰላም፣ በፍትህ እና በፖለቲካ እኩልነት የሚኖሩባት መኾኗን የሚያበስር አካታች (inclusive) መመርያ ይዘው ሥልጣን ላይ ወጡ። በርግጥ ይህ አካታች እሴት የሚመለከተው ደቡብ አፍሪካውያንን ብቻ ይኹን ወይም የውጪ ዜጎችን ይጨምር ግልጽ አልነበረም። በደንብ አልተተነተነም፤ ክርክር አልተደረገበትም። ነገር ግን በተለይ በዴሞክራሲው የመጀመርያ ዓመታት የኮንግረሱ አመራሮች በተግባር ሐሳቡ የውጪ ዜጎችንም እንዲጨምር አድርገውት ነበር። በእነዚሁ ዓመታት ለበርካታ ስደተኞች የመኖርያ ፈቃድ ተሰጥቷል። ደቡብ አፍሪካ ነጻነቷን ስትቀዳጅ በብዙ የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ ግጭት እሳቶች ይነዱ ነበር። ከእነዚህ ግጭቶች የሚያመልጡ በርካታ ስደተኞች አገሪቱን መጠለያ አደረጉ። በተጨማሪም ደቡብ አፍሪካ ከብዙ የአፍሪካ አገሮች የተሻለ የኢኮኖሚ የዕድገት ደረጃ ላይ ያለች እና የገቢ መሻሻል ዕድል የምትሰጥ በመኾኗ የኢኮኖሚ ስደተኞች ማግኔት ኾነች። ከሞዛምቢክ፣ ከዚምባቡዌ፣ እና ከኮንጎ በነፍስ ወከፍ በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ወደ አገሪቱ ገቡ። ከምዕራብ እና ምሥራቅ አፍሪካም ቢኾን ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ሰዎች ወደ ደቡብ አፍሪካ አቀኑ። ከእነዚህ ስደተኞች መካከል አብዛኞቹ ቀያቸው ያደረጓቸው ጥቁር ድኻ ደቡብ አፍሪካውያን የሚኖሩባቸውን ታውንሺፖች ነው። የስደተኞቹ የኢኮኖሚ ኹኔታዎች ከፍ እና ዝቅ ያለ ቢኾንም ጥናቶች እንደሚያሳዩት እነዚህ ስደተኞች በታውንሺፖች ያሉትን የኢኮኖሚ ችግሮች እና ኹከቶች ለመቋቋም ጠንካራ የዋስትና ማኅበራዊ መረቦችን ዘርግተዋል፤ በጥቃቅን ንግዶች እና በጥቁር ኢኮኖሚ በብዛት ይሳተፋሉ፣ እጅግ በዝባዥ በኾነ ዋጋ ተቀጥረው ሥራ ለመሥራትም አያቅማሙም።

በብዙ አገራት እንደምንመለከተው እነዚህ ሁለት ነገሮች- በመንግሥት የፖሊሲ ክሽፈት የተባባሰ ድህነት፣ ተስፋ መቁረጥ እና መጠነ ሰፊ ስደት- ሲገናኙ ማኅበራዊ ፈንጂ የመፈጠር ዕድሉ ከፍ ይላል። ፖለቲከኞች (ከፍተኛም ይኹን ዝቅተኛ እርከን ሥልጣን) በራሳቸው ድክመት የመጣ ችግርን ለመሸፈን ጣታቸውን ስደተኞች ላይ መጠቆማቸው ያልተለመደ ድርጊት አይደለም። በግጭት የሚጠቀሙ ነጋዴዎች (conflict entrepreneurs) ይህን አጋጣሚ አያልፉትም። ለምሳሌ፦ በ2008ቱ ኹከት ላይ የተሠሩ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ከኤኤንሲ ቀበሌ አደራጆች እስከ የታውንሺፕ ፖለቲካ እና ማኅበራዊ መዋቅር አንቀሳቃሾች በኹከት ቅስቀሳ ላይ ተሰማርተው ነበር። እነዚሁ ጥናቶች እንደሚያሳዩት የደቡብ አፍሪካውያን የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች ሲጨምሩ- የመዋቅሩ መሪዎች ድጋፍ እና ተደማጭነት እያሽቆለቆለ ሲመጣ – ስደተኞች ላይ የሚያደርጉት ቅስቀሳ ያይላል። የቅስቀሳዎቹ ዋነኛ ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦ የደቡብ አፍሪካ ድኾች ከችግራቸው ሊወጡ ያልቻሉት ሥራቸውን በስደተኞች ስለሚነጠቁ ነው፤ ገቢያቸው ከስደተኞች በሚመጣ ፉክክር ይቀንሳል፤ በስደተኞች መብዛት ምክንያት በመኖርያ ቤቶች አቅርቦት ላይ የሚደርሰው ጫና ከፍተኛ ነው። እነዚህ በሙሉ የአስተዳደርን ክሽፈት የሚደብቁ ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ የቀስተ ደመናዋ አገር የሚለው ሐሳብ ለደቡብ አፍሪካውያን እንጂ ለውጪ አገር ዜጎች አይሠራም የሚለው አጠቃላይ አመለካከት አግላይ ብሔረተኝነት (exclusive nationalism) በመፍጠር ልዩነቱን አባብሶታል። ከዴሞክራሲ የመጀመርያዎቹ ዓመታት ውጭ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት መሪዎች በንግግራቸው፣ በተግባራቸው እና በፖሊሲያቸው የቀስተ ደመናን ሐሳብ የውጪ ዜጎችን በሚያካትት ኹኔታ ለማስፋት ፍላጎት እንደሌላቸው አሳይተዋል።

የጥላቻ ቅስቀሳ፣ አሉታዊ እና አግላይ ብሔረተኝነት የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካለው ደኅንነትን የመጠበቅ ድክመት ጋር ተያይዞ በየጊዜው ስደተኛ ጠል ጥቃቶች እንዲጀመሩ እና በቀላሉ እንዲባባሱ ምክንያት ኾኗል። ለምሳሌ፦ የ2008ቱ ኹከት ሲቀጣጠል እና ሲስፋፋ የምቤኪ መንግሥት ለቀናት ከሩቅ ተመልካችነት ያለፈ ሚና አልነበረውም። በመጨረሻ ከብዙ ማመንታት በኋላ ኹከት ወዳለባቸው ሥፍራዎች ወታደሮችን በመላክ ጥቃቱን አስቁሞታል። የዙማ መንግሥትስ ይኼን ለማድረግ ምን ያህል ጊዜ ይፈጅበት ይኾን?

Source: ሰባት ኪሎ

The post የደቡብ አፍሪካው የስደተኛ ጠልነት መነሻው ምንድነው? (የሰባት ኪሎ ወቅታዊ አጭር ትንተና) appeared first on Zehabesha Amharic.

(የደቡብ አፍሪካና የየመን ጉዳይ) “ከራሳችን ውጪ ለችግራችን ደራሽ መንግስት የለንም!”የሰማያዊ ፓርቲ ወቅታዊ መግለጫ

$
0
0

የኢትዮጵያውያን የውርደት ዘመን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ሰሞኑን ከተከሰተው እጅግ አስከፊ ሁኔታ ላይ አድርሶናል፡፡ የመን ውስጥ በተከሰተው ጦርነት ተጎጂ የሆኑትን የውጭ ዜጎች መንግስታቶቻቸው ቀድመው ሲያስወጡ ለኢትዮጵያውያን ግን የሚደርስላቸው አልተገኘም፡፡ ይህንን ውርደትም ወገኖቻችን ‹‹የመን ውስጥ የቀረነው እኛና ውሻ ብቻ ነን፡፡›› ሲሉ እጅግ በሚያሳዝን መልኩ ገልጸውታል፡፡ ኢትዮጵያውያን ላይ የመድፍ፣ የሞርታርና የአውሮፕላን ድብደባ ሲዘንብባቸው በመከራ ላይ ያሉት ኢትዮጵያውያን ስልክ እንዲደውሉ በፌስ ቡክ ላይ በመለጠፍ ከማላገጥ ውጭ ምንም ያላደረገው የህዝብ ስልጣንን በሀይል የተቆጣጠርው ገዥው ፓርቲ ለራሱ ስልጣን ይጠቅሙኛል ያላቸውን የጦርነቱ ተሳታፊዎች ደግፎ መግለጫ ሲሰጥ የኢትዮጵያውያንን ስቃይ እጥፍ ድርብ አድርጎታል፡፡ በአጭሩ ኢህአዴግ ለራሱ ጥቅም ሲል ብቻ በማያገባውና በማይወጣው ዓለም አቀፍ ጦርነት ውስጥ ሀገራችንን ሲዘፍቅ ጦርነቱን ያወጀው የሚደርስላቸው ባጡ ምስኪን ኢትዮጵያውያንና በኢትዮጵያ ላይ ነው፡፡ ይህም የሀገራችን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ከመቸውም ጊዜ በላይ የወደቀና ለዜጎች እንደማይቆም በድጋሚ ገሃድ የወጣበት ነው፡፡
south africa ethiopians
በየመን የተከሰተውን መርዶ ሰምተን ሳንውል ሳናድር ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ አስደንጋጭ አደጋና እና ሰቆቃ ልንሰማ ተገደናል፡፡ ኢትዮጵያውያን ሀብትና ንብረታቸው መዘረፉ ሳያንስ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው ሲያልፍ በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ተከታትለናል፡፡ የዚህ አሰቃቂ አደጋ ሰለባ የሆኑ የሌሎች ሀገራት ዜጎች በቶሎ ከደቡብ አፍሪካ ሲወጡ፣ እንዲሁም ሀገራቱ ዜጎቻቸውን መታደግ ያስችላል ያሉትን መፍትሄዎች ሲያስቀምጡ እና ሲያስጠነቅቁ ቢደመጥም ኢህአዴግ ግን እንደተለመደው የኢትዮጵያውያንን ሰቆቃና ስቃይ ከምንም እንዳልቆጠረው በግልፅ እየታየ ነው፡፡

በእርግጥ ላለፉት 24 ዓመታት ኢህአዴግ ሀገር ውስጥ የሚኖሩትን ዜጎች ሲያሰቃይ፣ በውጭ የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያንም የሆነ ያልሆነ ስም እየለጠፈ በጠላትነት ሲፈርጃቸው እንደቆየ አይተናል፡፡ ከኢትዮጵያውያን ይልቅ የራሱን የግል ጥቅም ሲያሳድድም ቆይቷል፡፡ በቅርቡ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ወገኖቻችን ከፍተኛ በደል ሲደርስባቸው ይህ ነው የሚባል እገዛ ያላደረገው ኢህአዴግ ሰማያዊ ፓርቲ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን በደል በማውገዝ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኘው የሳውዲ ኤምባሲ ላይ ተገኝቶ ሲቃወም የሳውዲ ፖሊሶች ሀገራቸው ውስጥ ኢትዮጵያውያን ላይ ከፈፀሙት በደል ያልተናነሰ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሰልፍ በወጡት ኢትዮጵያውያን ላይ በጭካኔ ድብደባ ፈፅሟል፡፡ ይህም ኢህአዴግ ለኢትዮጵያውያን የቆመ ሳይሆን በበእድ አገራት በኢትዮጵያውያን ላይ በደል ከሚፈፅሙት ያልተናነሰ ጨካኝ ስርዓት መሆኑን ያሳየበት ነው፡፡

ኢህአዴግ ለስሙ ‹‹የዳያስፖራ ፎረም›› በሚል የራሱን ደጋፊዎች አደራጅቶ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ለልማት የበኩላቸውን እንዲያደርጉ እየሰራ እንደሚገኝ በስሩ በያዛቸው ሚዲያዎች ሲያሰራጭ ከርሟል፡፡ ከዚህም ባሻገር ኢትዮጵያውያኑ ለእነሱና ለሀገራቸው እንደማያስብ በመረዳታቸው ምክንያት ፊታቸውን ስላዞሩበት ውጤታማ አልሆነም እንጅ በተለያዩ አገራት እየተዘዋወረ ለአባይ ግድብ የበኩላቸውን እንዲያዋጡ ሲወተውት ታይቷል፡፡ ሳንቲም ለመልቀም በተለያዩ የዓለም ከተሞች እየዞረ ኢትዮጵያውያንን የሚሰበስበው ገዥው ፓርቲ በችግራቸው ወቅት ግን ምንም አይነት እርዳታ ሲያደርግ አይስተዋልም፡፡ ይብሱንም ችግር ላይ ባሉት ኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ በደል ሲፈጽምና በስቃያቸው ላይ የማላገጥ ያህል ፕሮፖጋንዳ ሲሰራባቸው እያየን ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው ገዥው ፓርቲ ኢትዮጵያውያንን አባብሎ ገንዘብ ከመቀበል ያለፈ ለውድ ህይወታቸው ደንታ እንደሌለው ነው፡፡

በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሱ ባሉት ተደጋጋሚ ግፎች ተሸፈነ እንጅ ሰሞኑን ሌላ ኢህአዴግ ለዜጎች እንደማይጨነቅ የታየበት ክስተት እየተፈፀመ እንደሆነ በተለያዩ ድህረ ገጾች ላይ ለመከታተል ችለናል፡፡ ኢህአዴግ ለራሱ ጥቅም ሲል ለሱዳን መንግስት አሳልፎ በሰጠው ሰፊና ለም የሀገራችን ሉዓላዊ መሬት አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ አሳፋሪ እና አሰቃቂ ወንጀል እንደተፈፀመ ተዘግቧል፡፡ የሱዳን መንግስት ወታደሮች ድንበሩን ጥሰው የሱዳን አዋሳኝ በሆነው የሰሜን ጎንደር ዞን ጠረፋማ ቦታዎች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች ላይ ጥቃት ሲፈፅሙ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ሊታደጋቸው አልቻለም፡፡

ሰሞኑን በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው ሰቆቃ ኢትዮጵያውያን አገራቸው ውስጥ ቢሆኑም ቢሰደዱም ከመከራው ሊላቀቁ እንዳልቻሉ አመላካች ነው፡፡ በውጭም ሆነ በሀገር ቤት የሚኖሩ የአንድ ሀገር ዜገች መብታቸውና ክብራቸው ሊጠበቅ የሚችለው ሀገር ውስጥ ለሀገርና ዜጎች የሚያስብና የሚቆረቆር መንግስት ሲኖር ነው፡፡ ሆኖም ኢትዮጵያውያን የሚገዙት ኢህአዴግን በመሰለ ለሀገርና ለህዝቡ ደንታ በሌለው ስርዓት በመሆኑ የሰሞኑ ሰቆቃ የሚገርም አይደለም፡፡ መቼውንም ኢህአዴግ የሀገርና የዜጎቹን መብትና ክብር ያስጠብቃል ብሎ መጠበቅም ዘበት ነው፡፡

ኢትዮጵያውያን የሀገራችንና የራሳችን ክብር እና ደህንነት ማስጠበቅ ካለብን መጀመሪያ ሀገራችን ላይ የሚገኘውን ስርዓት በፅኑ መታገል የግድ ይለናል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ምቹ አስተዳደር፣ ዴሞክራሲያዊና ለዜጎች የሚያስብ ስርዓት ቢኖር መጀመሪያውኑም ወገኖቻችን በገፍ ለአደጋ ወደሚጋለጡባቸው አካባቢዎች ባልተሰደዱ ነበር፡፡ በመሆኑም በቅድሚያ ክብራችንን ለማስመለስ የነፃነት ትግሉን አጠናክረን በመቀጠል፣ እንዲሁም በውጭ የምንገኝ ኢትዮጵያውያን ለጊዜውም ቢሆን ራሳችን ከአደጋ ለማዳን በተለያዩ ማህበራት ተደረጃቶ በመንቀሳቀስ ብሎም ስርዓቱ እስካለ ድረስ ችግሮቻችን እየተባባሱ እንጂ እየተቀረፉ እንደማይመጡ በመገንዘብ በሀገር ቤት ስርዓቱን ለመቀየር የሚደረገውን ሰላማዊ ትግል በማገዝ የችግራችንን ሁሉ መሰረት የሆነውን አምባገነናዊ አገዛዝ ለመለወጥ የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል፡፡ ክብራችንን ልናስመልስ የምንችለው ሀገራችን ውስጥ እንዳንኖር ያደረገንን ስርዓት ቀይረን አንድም በገዛ አገራችን መኖር ስንችል፣ አንድም በአደጋ ወቅት ሊደርስልን የሚችል ተቆርቋሪና ለዜጎች የሚያስብ መንግስት መመስረት ስንችል ብቻ መሆኑን ልንገነዘበው ይገባል፡፡

በአሁኑ ሰዓት በደቡብ አፍሪካ ሰቆቃ እየደረሰባቸው ያሉ ወገኖቻችንን ለመታደግ በዓለም ላይ ተበትናችሁ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በችግር ውስጥ ለወደቁት ወገኖቻችን አጋርነታችሁን በማሳየት ዓለማቀፍ የተቃውሞ ድምፃችሁን እንድታሰሙም ሰማያዊ ፓርቲ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ እልባት እንዲያገኝ ፓርቲያችን የበኩሉን ጥረት እያደረገ ሲሆን በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰውን በደል ለማስቆም አዲስ አበባ በሚገኘው የደቡብ አፍሪካ ኤምባሲ በኩል የራሱን ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ በሌላ በኩል የመን ውስጥና በሱዳን አዋሳኝ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ስርዓቱ ከባዕዳን ጋር ተባብሮ የሚፈፅመውን በደልም ለህዝብና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ በማጋለጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ መረጃዎችን እያሰባሰበ ይገኛል፡፡
በትግላችን የሀገራችንና የራሳችን ክብርና መብት እናስጠብቅ!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!
ሚያዝያ 9/2007 ዓ.ም

The post (የደቡብ አፍሪካና የየመን ጉዳይ) “ከራሳችን ውጪ ለችግራችን ደራሽ መንግስት የለንም!” የሰማያዊ ፓርቲ ወቅታዊ መግለጫ appeared first on Zehabesha Amharic.

ከራሳችን ውጪ ለችግራችን ደራሽ መንግስት የለንም! (በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ)

$
0
0

blue_party_ethiopia101370869814 (1)የኢትዮጵያውያን የውርደት ዘመን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ሰሞኑን ከተከሰተው እጅግ አስከፊ ሁኔታ ላይ አድርሶናል፡፡ የመን ውስጥ በተከሰተው ጦርነት ተጎጂ የሆኑትን የውጭ ዜጎች መንግስታቶቻቸው ቀድመው ሲያስወጡ ለኢትዮጵያውያን ግን የሚደርስላቸው አልተገኘም፡፡ ይህንን ውርደትም ወገኖቻችን ‹‹የመን ውስጥ የቀረነው እኛና ውሻ ብቻ ነን፡፡›› ሲሉ እጅግ በሚያሳዝን መልኩ ገልጸውታል፡፡ ኢትዮጵያውያን ላይ የመድፍ፣ የሞርታርና የአውሮፕላን ድብደባ ሲዘንብባቸው በመከራ ላይ ያሉት ኢትዮጵያውያን ስልክ እንዲደውሉ በፌስ ቡክ ላይ በመለጠፍ ከማላገጥ ውጭ ምንም ያላደረገው የህዝብ ስልጣንን በሀይል የተቆጣጠርው ገዥው ፓርቲ ለራሱ ስልጣን ይጠቅሙኛል ያላቸውን የጦርነቱ ተሳታፊዎች ደግፎ መግለጫ ሲሰጥ የኢትዮጵያውያንን ስቃይ እጥፍ ድርብ አድርጎታል፡፡ በአጭሩ ኢህአዴግ ለራሱ ጥቅም ሲል ብቻ በማያገባውና በማይወጣው ዓለም አቀፍ ጦርነት ውስጥ ሀገራችንን ሲዘፍቅ ጦርነቱን ያወጀው የሚደርስላቸው ባጡ ምስኪን ኢትዮጵያውያንና በኢትዮጵያ ላይ ነው፡፡ ይህም የሀገራችን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ከመቸውም ጊዜ በላይ የወደቀና ለዜጎች እንደማይቆም በድጋሚ ገሃድ የወጣበት ነው፡፡

በየመን የተከሰተውን መርዶ ሰምተን ሳንውል ሳናድር ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ አስደንጋጭ አደጋና እና ሰቆቃ ልንሰማ ተገደናል፡፡ ኢትዮጵያውያን ሀብትና ንብረታቸው መዘረፉ ሳያንስ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው ሲያልፍ በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ተከታትለናል፡፡ የዚህ አሰቃቂ አደጋ ሰለባ የሆኑ የሌሎች ሀገራት ዜጎች በቶሎ ከደቡብ አፍሪካ ሲወጡ፣ እንዲሁም ሀገራቱ ዜጎቻቸውን መታደግ ያስችላል ያሉትን መፍትሄዎች ሲያስቀምጡ እና ሲያስጠነቅቁ ቢደመጥም ኢህአዴግ ግን እንደተለመደው የኢትዮጵያውያንን ሰቆቃና ስቃይ ከምንም እንዳልቆጠረው በግልፅ እየታየ ነው፡፡

በእርግጥ ላለፉት 24 ዓመታት ኢህአዴግ ሀገር ውስጥ የሚኖሩትን ዜጎች ሲያሰቃይ፣ በውጭ የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያንም የሆነ ያልሆነ ስም እየለጠፈ በጠላትነት ሲፈርጃቸው እንደቆየ አይተናል፡፡ ከኢትዮጵያውያን ይልቅ የራሱን የግል ጥቅም ሲያሳድድም ቆይቷል፡፡ በቅርቡ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ወገኖቻችን ከፍተኛ በደል ሲደርስባቸው ይህ ነው የሚባል እገዛ ያላደረገው ኢህአዴግ ሰማያዊ ፓርቲ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን በደል በማውገዝ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኘው የሳውዲ ኤምባሲ ላይ ተገኝቶ ሲቃወም የሳውዲ ፖሊሶች ሀገራቸው ውስጥ ኢትዮጵያውያን ላይ ከፈፀሙት በደል ያልተናነሰ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሰልፍ በወጡት ኢትዮጵያውያን ላይ በጭካኔ ድብደባ ፈፅሟል፡፡ ይህም ኢህአዴግ ለኢትዮጵያውያን የቆመ ሳይሆን በበእድ አገራት በኢትዮጵያውያን ላይ በደል ከሚፈፅሙት ያልተናነሰ ጨካኝ ስርዓት መሆኑን ያሳየበት ነው፡፡

ኢህአዴግ ለስሙ ‹‹የዳያስፖራ ፎረም›› በሚል የራሱን ደጋፊዎች አደራጅቶ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ለልማት የበኩላቸውን እንዲያደርጉ እየሰራ እንደሚገኝ በስሩ በያዛቸው ሚዲያዎች ሲያሰራጭ ከርሟል፡፡ ከዚህም ባሻገር ኢትዮጵያውያኑ ለእነሱና ለሀገራቸው እንደማያስብ በመረዳታቸው ምክንያት ፊታቸውን ስላዞሩበት ውጤታማ አልሆነም እንጅ በተለያዩ አገራት እየተዘዋወረ ለአባይ ግድብ የበኩላቸውን እንዲያዋጡ ሲወተውት ታይቷል፡፡ ሳንቲም ለመልቀም በተለያዩ የዓለም ከተሞች እየዞረ ኢትዮጵያውያንን የሚሰበስበው ገዥው ፓርቲ በችግራቸው ወቅት ግን ምንም አይነት እርዳታ ሲያደርግ አይስተዋልም፡፡ ይብሱንም ችግር ላይ ባሉት ኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ በደል ሲፈጽምና በስቃያቸው ላይ የማላገጥ ያህል ፕሮፖጋንዳ ሲሰራባቸው እያየን ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው ገዥው ፓርቲ ኢትዮጵያውያንን አባብሎ ገንዘብ ከመቀበል ያለፈ ለውድ ህይወታቸው ደንታ እንደሌለው ነው፡፡

በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሱ ባሉት ተደጋጋሚ ግፎች ተሸፈነ እንጅ ሰሞኑን ሌላ ኢህአዴግ ለዜጎች እንደማይጨነቅ የታየበት ክስተት እየተፈፀመ እንደሆነ በተለያዩ ድህረ ገጾች ላይ ለመከታተል ችለናል፡፡ ኢህአዴግ ለራሱ ጥቅም ሲል ለሱዳን መንግስት አሳልፎ በሰጠው ሰፊና ለም የሀገራችን ሉዓላዊ መሬት አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ አሳፋሪ እና አሰቃቂ ወንጀል እንደተፈፀመ ተዘግቧል፡፡ የሱዳን መንግስት ወታደሮች ድንበሩን ጥሰው የሱዳን አዋሳኝ በሆነው የሰሜን ጎንደር ዞን ጠረፋማ ቦታዎች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች ላይ ጥቃት ሲፈፅሙ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ሊታደጋቸው አልቻለም፡፡

ሰሞኑን በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው ሰቆቃ ኢትዮጵያውያን አገራቸው ውስጥ ቢሆኑም ቢሰደዱም ከመከራው ሊላቀቁ እንዳልቻሉ አመላካች ነው፡፡ በውጭም ሆነ በሀገር ቤት የሚኖሩ የአንድ ሀገር ዜገች መብታቸውና ክብራቸው ሊጠበቅ የሚችለው ሀገር ውስጥ ለሀገርና ዜጎች የሚያስብና የሚቆረቆር መንግስት ሲኖር ነው፡፡ ሆኖም ኢትዮጵያውያን የሚገዙት ኢህአዴግን በመሰለ ለሀገርና ለህዝቡ ደንታ በሌለው ስርዓት በመሆኑ የሰሞኑ ሰቆቃ የሚገርም አይደለም፡፡ መቼውንም ኢህአዴግ የሀገርና የዜጎቹን መብትና ክብር ያስጠብቃል ብሎ መጠበቅም ዘበት ነው፡፡

ኢትዮጵያውያን የሀገራችንና የራሳችን ክብር እና ደህንነት ማስጠበቅ ካለብን መጀመሪያ ሀገራችን ላይ የሚገኘውን ስርዓት በፅኑ መታገል የግድ ይለናል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ምቹ አስተዳደር፣ ዴሞክራሲያዊና ለዜጎች የሚያስብ ስርዓት ቢኖር መጀመሪያውኑም ወገኖቻችን በገፍ ለአደጋ ወደሚጋለጡባቸው አካባቢዎች ባልተሰደዱ ነበር፡፡ በመሆኑም በቅድሚያ ክብራችንን ለማስመለስ የነፃነት ትግሉን አጠናክረን በመቀጠል፣ እንዲሁም በውጭ የምንገኝ ኢትዮጵያውያን ለጊዜውም ቢሆን ራሳችን ከአደጋ ለማዳን በተለያዩ ማህበራት ተደረጃቶ በመንቀሳቀስ ብሎም ስርዓቱ እስካለ ድረስ ችግሮቻችን እየተባባሱ እንጂ እየተቀረፉ እንደማይመጡ በመገንዘብ በሀገር ቤት ስርዓቱን ለመቀየር የሚደረገውን ሰላማዊ ትግል በማገዝ የችግራችንን ሁሉ መሰረት የሆነውን አምባገነናዊ አገዛዝ ለመለወጥ የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል፡፡ ክብራችንን ልናስመልስ የምንችለው ሀገራችን ውስጥ እንዳንኖር ያደረገንን ስርዓት ቀይረን አንድም በገዛ አገራችን መኖር ስንችል፣ አንድም በአደጋ ወቅት ሊደርስልን የሚችል ተቆርቋሪና ለዜጎች የሚያስብ መንግስት መመስረት ስንችል ብቻ መሆኑን ልንገነዘበው ይገባል፡፡

በአሁኑ ሰዓት በደቡብ አፍሪካ ሰቆቃ እየደረሰባቸው ያሉ ወገኖቻችንን ለመታደግ በዓለም ላይ ተበትናችሁ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በችግር ውስጥ ለወደቁት ወገኖቻችን አጋርነታችሁን በማሳየት ዓለማቀፍ የተቃውሞ ድምፃችሁን እንድታሰሙም ሰማያዊ ፓርቲ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ እልባት እንዲያገኝ ፓርቲያችን የበኩሉን ጥረት እያደረገ ሲሆን በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰውን በደል ለማስቆም አዲስ አበባ በሚገኘው የደቡብ አፍሪካ ኤምባሲ በኩል የራሱን ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ በሌላ በኩል የመን ውስጥና በሱዳን አዋሳኝ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ስርዓቱ ከባዕዳን ጋር ተባብሮ የሚፈፅመውን በደልም ለህዝብና ለዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ በማጋለጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ መረጃዎችን እያሰባሰበ ይገኛል፡፡

በትግላችን የሀገራችንና የራሳችን ክብርና መብት እናስጠብቅ!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!

ሚያዝያ 9/2007 ዓ.ም

The post ከራሳችን ውጪ ለችግራችን ደራሽ መንግስት የለንም! (በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ) appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ቁጥቡ እንግሊዛዊ የሊቨርፑል አጥቂ ስተሪጅ ማነው?

$
0
0

sturridge

ዳንኤል ስተሪጅ ራሱን እየገለፀ ነው፡፡ ስለ ሰብዕናው ለማብራራት ሞከረ፡፡ ባህሪው በምን አይነት መንገድ እንደተቀረፀ ለመተንተን ጣረ፡፡ ገለፃውን የጀመረው በርሚንግሃም ውስጥ በሆክሌይ ጎዳናዎች አቆራርጦ ወደ ትምህርት ቤት ስለሚጓዘው የ10 ዓመት ታዳጊ በማውሳት ነው፡፡ የወሮበሎች ጥቃት እንግዳ ባልሆነበት አካባቢ ታዳጊው እራሱን ከአደጋ ለመጠበቅ ያደርግ የነበረውን ሁሉ ያስታውሳል፡፡ ታዳጊው እንዴት ራሱን ደፍቶ መንቀሳቀስ እንደለመደ አይዘነጋም፡፡ ሰዎች ጋር አይን ለአይን ላለመተያየት ያደርግ የነበረው ጥንቃቄ አይረሳውም፡፡ የሆነ ሰው ቢጠራው ዞሮ አይመለከትም አልያም ሰላምታ አያቀርብም፡፡ ዝም ብሎ ጉዞውን ይቀጥላል፡፡ አዲስ ወይም እንግዳ የሆነ ሰው ሁሉ በጥርጣሬ ይታያል፡፡ ለወዳጅነትም አይታጭም፡፡

የታዳጊው የተለመደ ተግባር ያ ነበር፡፡ ጠዋት መኖሪያ ቤቱ ከሚገኝበት ሆክሊይ ትምህርት ቤቱ ወዳለበት ኒውታውን ወደተባለ የከተማው ክፍል ይሄዳል፡፡ ከሰዓት በዚያው መንገድ ወደ ቤቱ ይመለሳል፡፡ ቤተሰቦቹ አብረውት ነበር፡፡ ጥብቅ ግንኙነት የነበራቸው ጓደኞችም ነበሩት፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ከእግርኳስ ተለይቶ አያውቅም፡፡ በዚያ ምክንያት ከብዙ ነገሮች ተገልሎ በግሉ ዓለም ውስጥ መኖርን ተካነበት፡፡
ስተሪጅ አሁን 25 ዓመት ሆኖታል፡፡ የሊቨርፑል እና እንግሊዝ ኮከብ ተጨዋች ነው፡፡ ነገር ግን አሁንም ድረስ ያ ታዳጊ በውስጡ ይኖራል፡፡ ወደ እውቅና የመጣ ሰሞን ‹‹ቁጡ›› ተብሎ ሲገለፅ የነበረው ለዚያ ሊሆን እንደሚችል ያምናል፡፡ ቁጡ አይደለም፡፡ በብዙ መንገድ የዚያ ተቃራኒ ነው፡፡ አስደሳች እና ሰው አክባሪ ነው፡፡ ነገር ግን የተወሰነ ቁጥብነት ይታይበታል፡፡ በአብዛኛው ኮስታራ መስሎ ይታያል፡፡ ግንባሩ አይፈታም፡፡ በፌዝ እ በቀልድ በሚታወቀው የእግርኳሱ ዓለም ባልተለመደ መልኩ ገለልተኝነት ይታይበታል፡፡

‹‹ጥበብ ያለ ዓለም ያለኝ ሰው ነኝ፡፡ የጓደኞቼ ቁጥር ከአንድ እጅ ጣቶች አይበልጥም፡፡ ሁሉም ሰው በሥራ አጋጣሚ የሚተዋወቃቸው ሰዎች፣ የቡድን ጓደኞች እና የመሳሰሉት ይኖሩታል፡፡ ነገር ግን ከዚያ ውጪ ባለው ህይወቱ ከቤተሰቦቼ ሌላ በዙሪያዬ ያሉ ሰዎች በጣም ጥቂት ናቸው›› ይላል ስተሪጅ፡፡

‹‹እንደሚመስለኝ ያ የሆነው በአስተዳደጌ ምክንያት ነው፡፡ በተወሰኑ አካባቢዎች ስታድግ ድምፅህ በጉልህ እንዲሰማ ወይም ለቀቅ ያለ የአኗኗር ዘይቤ እንዲኖርህ አትፈልግም፡፡ ምክንያቱም ያንን ማድረግህ ለማትፈልገው ነገር ሊያጋልጥህ ይችላል፡፡ እኔ ባደግኩበት አካባቢ ወንጀል እና ሌሎች ተዛማጅ ነገሮች ተንሰራፍቶ ነበር፡፡ በርሚንግሃም ጥሩ ከተማ ነው፡፡ ሆኖም ባደረግኩበት አካባቢ ከአዲስ ሰዎች ጋር መተዋወቅ እና ወዳጅነት ለመመስረት አይደለም፡፡ የሆነ ጥቃት ሊሰነዝሩብህ እንጂ፡፡

‹‹በበሚንግሃም ታዳጊ ሳለሁ የወሮበሎች ባህል በከተማው ተንሰራፍቶ ነበር፡፡ ከዚያ ርቆ መቆየት ቀላል ነበር፡፡ ምክንያቱም እግርኳስ አለና፡፡ ነገር ግን ከዚያን ጊዜ ወዲህ ከሰዎች ጋር ብዙም የማልቀላቀል ሰው ሆንኩ፡፡ እንደዚያ ማድረግ ሁለተኛ ተፈጥሮዬ ሆነ፡፡ ሁልጊዜ ተጠራጣሪ መሆን ነበረብኝ፡፡ ውንብድናው የቆዳ ቀለምን መሰረት ያደረገ አልነበረም፡፡ ይበልጥ በአካባ የተከፋፈለ ነው፡፡ በሆነ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚሳተፍ ሰው የቤተሰብህ ወዳጅ ሊሆን ሁሉ ይችላል፡፡ እኔ በዚያ መሰሉ እንቅስቃሴ ውስጥ ፈፅሞ ተሳትፎ አልነበረኝም፡፡ በዚያ አካባቢ በማደግ ደስተኛ ነኝ፡፡ ለማደግ የሚረዳ ጥሩ ስፍራ ነው፡፡ መቼም ቢሆን አቃልዬ ልገልፀው አልችልም፡፡ ቤቴ ነው፡፡ አካባቢውን እወደዋለሁ፡፡ በዚያ ከፍተኛ የሆነ የካሪቢያን ባህል አለ፡፡ ምግቡ እና ሁሉም ነገር አስደሳች ነው›› የሊቨርፑሉ አጥቂ ንግግሩን ይቀጥላል፡፡

ስተሪጅ በቀላሉ ሊገለፅ የሚችል ሰው አይደለም፡፡ ስለ እርሱ ማውራትን አስደሳች የሚያደርገው አንደኛውነገር ያ ነው፡፡ በሊቨርፑል ከፍተኛ ቦታ ከሚሰጣቸው ተጨዋቾች አንዱ ነው፡፡ ከቡድኑ መሪዎች እንደ አንዱ ይታያል፡፡ ወጣት ተጨዋቾ እርዳታ እና ምክር ፍለጋ ወደ እርሱ ይመጣሉ፡፡ እርሱም ቢሆን ምክር የሚግለሳቸው በደስታ ነው፡፡ እንደዚያም ሆኖ ብቸኛ እንደሆነ ያስባል፡፡

በከተማዋ እምብርት በሚገኝ ህንፃ ብቻውን ይኖራል፡፡ አንዳንዶች ጎል ካገባ በኋላ ደስታውን የሚገልፅበትን መንገድ ተመልክተው ማህበራዊ ኑሮ የሚወድድ እና ወጣ እያለ የሚዝናና አድርገው ይቆጥሩታል፡፡ ነገር ግን እንደዚያ አይነት ሰው እንዳልሆነ ይናገራል፡፡ ከፊሎቹ ከልዊስ ቶምሊንሰን አልያም ቲኒ ቴምፓህ ጋር የተነሳውን ፎቶ ተመልክተው እዩኝ እዩኝ ማለት እንደሚወድድ ይገምታሉ፡፡ ነገር ግን እርሱ ያን አይነት ፍላጎት እንደሌለው ማረጋገጫ ይሰጣል፡፡ ሌሎች ግልፅ አድርገው ይቆጥሩታል፡፡ በዚህም ቢሆን አይስማማም፡፡

ከአብዛኞቹ ተጨዋቾች በተሻለ አስተዋይ እና ዝምተኛ ነው፡፡ የተወሰኑ ሰዎችን ምቾት የሚነሳቸው ያ ይመስላል፡፡ ‹‹ከአዳዲስ ሰዎች ጋር ስገናኝ በራሴው ዛቢያ ላይ የምሽከረከር ይመስለኛል›› በማለት ይናገራል፡፡ በሌሎ መንገዶችም የተለየ ነው፡፡ ብዙውን ጊዜ ከሊቨርፑል የልምምድ ሜዳ ወደ ቤቱ የሚመለሰው በቅንጡ መኪኖች ሳይሆን በታክሲ ነው፡፡ ከጉዳቱ ለማገገም በዩናይትድ ስቴትስ ቆይታ ባደረገበት ወቅትም ቢሆን ከእያንዳንዱ ዕለት ህክምና በኋላ የሚያመራው ወደ ቅንጡ ሬስቶራንቶች አልያም ዘመናዊ ባር አልነበረም፡፡
‹‹ጠዋት አንድ ሰዓት አካባቢ እነሳለሁ፡፡ አስር ወይም አስራ አንድ ሰዓት አካባቢ የዕለቱን መርሃ ግብር አጠናቅቃለሁ፡፡ ያን ጊዜ መጨላለም ይጀምራል፡፡ ፀሐይ መጥለቅ ትጀምራለች፡፡ ያን ጊዜ ወደ ክፍሌ እመለሳለሁ፡፡ እመገባለሁ፡፡ የተወሰነ ጊዜ ዶሚኖ እጫወት እና ወደ መኝታዬ አመራለሁ››

ጉዳት የስትሪጅን የውድድር ዘመን ጉዞ አስተጓጉሎበታል፡፡ በ2013/14 የውድድር ዘመን በስምንት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ጎል በማስቆጠር ክብረወሰን ተጋርቷል፡፡ ከልዊስ ሱአሬዝ ጋር አስፈሪ የአጥቂ መስመር ጥምረት ፈጥሯል፡፡ ከዚያ በኋላ ባጋጠመው ተደራራቢ ጉዳት ምክንያት ለአምስት ወራት ከሜዳ ለመራቅ ተገደደ፡፡

የሱአሬዝ ለባርሴሎና መሸጥ ከእርሱ አለመኖር ጋር ተደማምሮ ሊርፑል የውድድር ዘመኑን በመጥፎ ሁኔታ እንዲጀመር አስገድዶታል፡፡ ስተሪጅ በጃንዋሪ መጨረሻ ወደ ቡድኑ የተመለሰ ሲሆን የሊቨርፑሉ አሰልጣኝ ብሬንዳን ሮጀርስ ብልጠት በሚታይበት መልኩ እየተጠቀሙበት ይገኛሉ፡፡ የሜርሲ ሳይዱ ክለብ እስከ አራተኛ ያለውን ደረጃ ይዞ ለማጠናቀቅ በሚያደርገው ጥረት የእንግሊዛዊው መመለስ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወትም ይታሰባል፡፡ ሮይ ሆጅሰን ወደ እንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ይመልሱት እንደሆነም የሚታወቀው ዛሬ (ማክሰኞ) ነው፡፡ ከሎቲንያ እና ጣልያን ብሔራዊ ቡድን ጋር የሚጫወተውን ቡድናቸውን አባላት ይፋ ሲያደርጉ ከስተሪጅ ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት ዳግም ትኩረት ያገኛል፡፡ አጥቂው የውድድር ዘመኑን ያደበዘዘበትን የመጀመሪያ ጉዳት ያስተናግደው በሴንት ጆርጅ ፓርክ ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር ልምምድ በሚሰራበት ወቅት ነበር፡፡

በሊቨርፑል ሮጀርስ ከጨዋታ በኋላ ሁለት የማገገሚያ ቀናትን ይፈቅዳሉ፡፡ ነገር ግን ሆጅሰን ተጫዋቾቻቸው በሁለተኛው ቀን ልምምድ እንዲሰሩ ይጠይቃሉ፡፡ በሴፕቴምበር 3 ረቡእ እንግሊዝ ኖርዌን ባሸነፈችበት የዌምብሌይ ጨዋታ ስተሪጅ ለ83 ደቂቃዎች በሜዳ ውስጥ ቆይቷል፡፡ አርብ ዕለት ሴፕቴምበር 5 ከብሔራዊ ቡድን ጋር አፈትልኮ የመሮጥ ልምምድ ሲሰራ በታፋው ጡንቻ ላይ ጉዳት ደረሰበት፡፡
የተለመደው የክለብ እና ብሔራዊ ቡድን ንትርክም ተጀመረ፡፡ አንዳንዶች እንዲያውም ስተሪጅ ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የአሰልጣኞች ስታፍ አባላት ለልምምድ ዝግጁ አለመሆኑን እንደነገራቸው ነገር ግን የሚሰማው እንዳላገኘ ይናገራሉ፡፡ ሆጅሰን ግን ስተሪጅ ልምምዱን ለመስራት አለመፈለጉን እንዳላሳወቃቸው ይናገራሉ፡፡ ንትርኩ ግን ተባብሶ ቀጥሏል፡፡ ስተሪጅም በዝምታው ገፍቶበታል፡፡ አጋጣሚውን በግልፅ ለመናገር ዝግጁ አይደሉም፡፡ አሁን ሙሉ በሙሉ ጤነኛ ነው፡፡በሆዱ ምንም አይነት መጥፎ ስሜት አለመኖሩንም ይገልፃሉ፡፡ ሆጅሰንንም ለጉዳቱ ተጠያቂ አያደርግም፡፡

‹‹ከዚህ በፊት ምንም አይነት ነገር ቢከሰት ለእንግሊዝ መጫወት ያስደስተኛል፡፡ አጋጣሚው ተከስቷል፡፡ ነገር ግን ያለፈ ታሪክ ነው፡፡ ሳስታውሰው ልኖር አልፈልግም፡፡ የእግርኳስ ህይወት እንደዚያ ነው፡፡

‹‹ከብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ጋር መልካም ግንኙነት አለን፡፡ ምንም የሚያስጨንቅ ነገር የለም፡፡ የፅሑፍ መልዕክቶችን እንለዋወጣለን፡፡ በአካል ተገናኝተንም እንነጋገራለን፡፡ ግንኙነታችን አልተቋረጠም፡፡ በጉዳት ላይ በነበርኩባቸው ጊዜያት ሁሉ ከጎኔ አልተለየም፡፡ ላጋጠመኝ ጉዳት እርሱን ተወቃሽ አላደርግም፡፡ ሌሎቹ አሰልጣኝ ቡድኑ አባላትም ተጠያቂ ሊደረጉ አይችሉም፡፡ ጉዳቱ ከመጥፎ ዕድል ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ለእርሱም ሆነ በዙሪያው ላሉት ሰዎች ከፍተኛ ክብር እና አድናቆት አለኝ፡፡ ግንኙነታችን በጣም ሰላማዊ ነው፡፡

‹‹ለእኔ ከጨዋታ በኋላ የሚደረግ የሁለት ቀን እረፍት ይስማማኛል፡፡ ነገር ግን እኔ ሁሉንም ተጨዋቾች ልወክል አልችልም፡፡ እያንዳንዱ ተጨዋች የተለየ ልማድ አለው፡፡ በሁለተኛው ቀን መለማመድ የሚወድድ አለ፡፡ አንዳንዶች ያ አይመቻቸውም፡፡ በአሁኑ ወቅት የሁለት ቀን የማገገሚያ እረፍትን ለምጄያለሁ፡፡ አንድን ነገር ስትለማመደው ይዋሃድሃል፡፡ ሁለት ከድካም የማገገሚያ የእረፍት ቀናት በማይሰጥባቸው ክለቦች ውጤታማ ለመሆን ተቸግሬያለሁ፡፡ በመሆኑ የአሰልጣኝ እርምጃ ያልተለመደ አይደሉም›› ስተሪጅ አስተያየቱን ይቀጥላል፡፡
‹‹በየትኛውም አካባቢ ብትሆን ሁኔታውን በፀጋ መቀበል አለብህ፡፡ በማንም ላይ ጣቴን አልቀስርም፡፡ ከእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ጋር የትኛውንም ነገር እንድፈፅ ቢያዘኝ አደርገዋለሁ፡፡ ምክንያቱም አለቃው እርሱ ነው፡፡ እግሯስ የቡድን ሥራ ነው፡፡ ልጆቹ የሚሰሩትን ሁሉ መፈጸም ይጠበቅብሃል፡፡ ያንን መቀበል ይኖርብሃል፡፡ በዚህ ምክንያት ማንንም አልወቅስም››

እናንተ እንደፈለጋችሁ ተርጉሙት፡፡ ስተሪጅ ለወቀሳ የሚጣደፍ ሰው አይደለም፡፡ ቆራጥ እና እልኸኛ መሆኑ አይካድም፡፡ ነገር ግን ቂመኛ አይደለም፡፡ በእምነቱ የፀና ክርስቲያን ነው፡፡ ከሜዳ ርቆ በነበረበት ወቅት ከተጋፈጣቸው ችግሮች የቀሰመውን ትምህርት ሲያስረዳ ድምፁ የወንጌላዊ ቃና ይላበሳል፡፡ ‹‹ከዚህ በፊት ስላደረገልኝ እና ወደፊት በህይወቴ ስለሚሰራው ነገር ሁሉ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ›› ይላል የሊቨርፑሉ አጥቂ፡፡ ‹‹የምትወድቅባቸው እንደዚሁም የምትነሳባቸው ጊዜያት አሉ፡፡ ሁሉም ነገር ሁልጊዜ አልጋ በአልጋ አይሆንም፡፡ በህይወትህ አልፎ አልፎ የሚከሰቱ ሰብዕናህን፣ ፅናትህን፣ እምነትህን በራስህ ላይ ያለህን እምነት እና የመሳሰሉትን የሚፈታተኑ ሁኔታዎች ውስጥ እንድታልፍ የምትገደድባቸው አጋጣሚዎች አሉ፡፡

‹‹በአዕምሮዬ ጥርጣሬ የሚባል የለም፡፡ በራስ እምነት አለኝ፡፡ በእግዚአብሔር አምናለሁ፡፡ እምነት አለኝ፡፡ በችሎታዬም እተማመናለሁ፡፡ በምንም ነገር አልጨነቅም፡፡ ጎሎችን በቋሚነት ማስቆጠሬን እንደምቀጥል አምናለሁ፡፡ በሁሉም ጨዋታዎች ላይ መሰለፍ እንደምችልም እተማመናለሁ››

ስተሪጅ ባልነበረባቸው ጊዜያት እግርኳስ ባለበት አልቆመም፡፡ ሆጅሰን በሚመርጡት የአጥቂ መስመር የመግባት ዕድል ያላቸው ተጨዋቾች ተበራክተዋል፡፡ ዳኒ ኢንግስ እና ቻርሊ ኦስቲን በዚህ ተርታ ይሰለፋሉ፡፡ አሰልጣኙ የስኳዳቸውን አባላት ይፋ ሲያደርጉ ተመረጠም አልተመረጠም ከፍተኛውን ትኩረት የሚወስደው ሃሪ ኬን መሆኑ ግን አይካድም፡፡ ስትሪጅ አዲስ ተፎካካሪ ተፈጥሮበታል፡፡ የተጫዋቹ አድናቂ እንደሆነ ሲጠየቅ ‹‹የሌሎች ሰዎችን ድልና ስኬት የምከታተልበት ምክንያት ምንድን ነው? ተጨዋቾች የሚሰሩት ነገር እና በቡድኑ ውስጥ የሚኖራቸው ቦታ አያስጨንቀኝም፡፡ ለእኔ ትርጉም የለውም፡፡ ሌሎችን በመመልከት በህይወትህ የትም አትደርስም፡፡ ምክንያቱም ከራስህ ጋር ግብግብ ትፈጥራለህ፡፡ ሃሪ ኬን ለፈፀመው ገድል እና ላሳካው ስኬት እንኳን ደስ ያለህ ልለው እችላለሁ፡፡ ነገር ግን እየሰራ ያለውን ነገር እየተከታተልኩ አይደለም፡፡ በራሴ እምነት አለኝ›
ስተሪጅ በስሱ ፈገግ አለ፡፡ ነገር ግን ልቡ በፍጥነት የምትመታ ይመስላል፡፡ ለጊዜው መጋረጃውን መልሷል፡፡ በሃሳቡ ራሱን የሚመለከተው በሆክሌይ ጎዳና ተግዳሮቶችን ለማሸነፍ አንገቱን ደፍቶ ብቻውን እንደሚጓዝ ታዳጊ ነው፡፡

The post Sport: ቁጥቡ እንግሊዛዊ የሊቨርፑል አጥቂ ስተሪጅ ማነው? appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ወደ ልዩ የወንድነት ቀመር የሚያመጡዎት ነጥቦች፡- ግዙፉ ደረት መገንቢያ 10 ምስጢሮች

$
0
0

በእጃችን ያለውን መፍትሄ ወደ ጎን በመተው ተቃራኒ ፆታን ለመማረክ አቅሙ ጎድሎን ከሆነ ከራሳችን ውጪ ማንንም ተጠያቂ ማድረግ አንችልም፡፡ የፍቅር ግንኙነታችንን ከሚወስኑና ተቃራኒ ፆታን የመማረክ ደረጃችንን ማሳደግ ከሚረዱን መሰረታዊ ጉዳዮች መካከል ጊዜና አቅሙ በሚፈቅድልን መጠን አካላችንን በስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማጎልበት አንዱ መንገድ ነው፡፡ በእርግጥ ፍቅርና እርስ በርስ መተሳሰብ የግንኙነት ማጠናከሪያ መሰረታዊ ነጥቦች መሆናቸውን የዘነጋ አይደለም ምክረ ሐሳባችን፡፡ ይልቁንም ከፍቅረኛና የትዳር አጋር ጋር የሚደረግን ጉዞ ጥርጊያውን የሚያበጅ እንደሆነ በማሰብ ነው፡፡
attractie
ባለፈው ሳምንት ዓብይ ጉዳያችን ፍቅር፣ ወሲብ፣ ልጅ፣ ገንዘብ እና ዕድሜን ስለሚወስነውና ሴቶችን ወንዶች ስለተሰሩበት ልዩ ቀመር ከምርምር ሐሳቦች በመነሳት አንባቢዎች ያሉበትን ቦታ እንዲመለከቱ ያስቻለ ሐሳብ ቀርቧል፡፡ በቀረበው ጽሑፍ ከአብባቢያን ለደረሱን ገንቢ ሐሳቦች በማመስገን ወደ ልዩ ቀመሩ የሚመራንን ምክረ ሐሳብ እንድናመለክታቸው ጠይቀውናል፡፡

ወንዶች ለሴቶች የመከታነታቸውና፣ የወንዳ ወንድነታቸው ውጤት የሆነው ወርቃማው ቁጥራቸው 1.6 መሆኑን ባለፈው ሳምንት ተመልክተናል፡፡ ለፆታ ተጣማሪያቸው መከታና አጋርነታቸው ማሳያ ተደርጎም የተወሰደ ሲሆን፣ መለኪያው ወንዱ የወንዱ ፆታና ባህሪ እንዲኖረው የሚያደርገው የቴስቴስትሮን ሆርሞን ትክክለኛ ምጣኔ በውስጣቸው እንዳለ የሚጠቁም ነው፡፡ በቀረበው ሐሳብ ታዲያ፣ ይህ ቁጥር ትከሻና ደረተ ሰፊ ወንዶች ጋ የመገኘት ምጣኔው ሰፊ መሆኑን ነው የተመከተው፡፡

በዚህ ሳምንት ከተፈጥሯዊው አጋጣሚ ውጪ ወደዚህ ቁጥር ሊያመጡን ከሚችሉ መንገዶች መካከል፣ ለወንዶች ብቻ የሚመከረውን የደረት አካባቢ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ቀላል በሆነ መንገድ ማካሄድ የሚችሉበትን መንገድ 12 በሚደርሱ ሐሳቦ ልናመለክታችሁ ወድደናል፡፡

1. ትዕግስት፡- ከመጽሔቶች እና ከተለያዩ ፀሀፍት ጡንቻን ፈጣን በሆነ ሂደት መገንባት በሚቻልበት መንገድ ዙሪያ በርካታ ሐሳቦ ቀርበው ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን ወደ ተግባር መግባትን እንደ አማራጭ ከወሰድን፣ ሂደቱ ዝግመታዊ ስለመሆኑ በቅድሚያ ግንዛቤ መያዝ ያስፈልግዎታል፡፡ ምናልባት የአንድ ዓመት የልፋት ውጤት ይጠይቀናል የሚሉት ባለሙያዎች፣ በዚህ ዓመት አሊያም እየተቃረበ ባለው ሌላኛው ዓመት ትልቅ ደረት ከፈለጉ ልንረዳዎት አንችልም ባይ ናቸው፡፡ ‹‹የትዕግስት ጉዳይ አሳሳቢ ከሆነብዎት ከዚህ ምክረ ሐሳብ ይልቅ 97 ዶላር የሚያስከፍለውን big muscle shortcuts.com›› ፕሮግራምን ቢጎበኙ ያዋጣዎታል፡፡ በአንፃሩ ረዥም ደረት በረዥም ጊዜ መስራትን ከመረጡ ያለምንም ክፍያ ደረተ ሰፊነትና ጠንካራነትን በምን መልክ ማምጣት የሚችሉበትን መንገድ ላሳያችሁ ይሏችኋል ባለሙያዋ፡፡

2. የማሟሟቂያ እንቅስቃሴ ማድረግን አይዘንጉ፡፡ የደረት ስፖርትን በሚያከናውኑበት ወቅት፣ በርካቶች ወንበርና ክብደቶችን መግፋት ብቻውን በቂ እንደሆነ በማሰብ ከፍተኛ ስህተት ይፈጽማሉ፡፡ ምንም አይነት የክብደት መግፋት ስፖርት ውስጥ ተሳትፈው የማያውቁ ሰዎች ሳይቀሩ፣ ፊልሞች ላይ በሚመለከቱት ብቻ እንቅስቃሴውን ማድረግ ላይከብዳቸው ይችላል፡፡ ነገር ግን ትክክለኛውን መንገድ ላያውቁት ይችላሉ፡፡ ጀማሪዎች ለጤና ጠንቅ በሆነ መንገድ የክብደት እንቅስቃሴ ውስጥ ሊገቡ ሁሉ ይችላሉ፡፡ ቀደም ሲል እንደተቀመጠው በፊልሞች እና በተለያዩ አጋጣሚዎች ሌሎች አካላት ስላደረጉት ብቻ የምንፈልገውን ዓይን ሳቢና ጠንካራ ደረቅ ለማምጣት የሰውነት ማሟሟቂያ እንቅስቃሴዎችን በቅድሚያ ማድረግ ነው፡፡

ባለሙያዋ በዚህ ረገድ ወደ ተግባር የሚገቡ አካላት የደረታቸውን አካባቢ በማቀያየር የማፍታታት ስራዎችን እንዲሁም የመግፋት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን ማስቀደም እንደሚያስፈልግ ይመክራሉ፡፡

3. በየቀኑ ወይም በተመሳሳይ ሁኔታ በትከሻቸውና በደረታቸው ላይ የሚሰሩ አካላት ከፍተኛ የግፊት እንቅስቃሴ ስለሚጠይቅ እና በትከሻ ላይ ድካ ስለሚያስከትል፣ ደረታችን ላይ የምንፈልገውን ለውጥ ለማምጣት አቅም እንድናጣ ምክንያት ይሆናል፡፡

4. አቅምዎን ይወቁ፡- ብዙ ሰዎች ትልቅ ደረትን ማምጫው መንገድ የእጅ እና የደረት እንቅስቃሴን በሚል ይደክማሉ፡፡ ግን እንቅስቃሴው ትልቅ ስህተት ተብሏል፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ካሉም በፍጥነት ትክክለኛውን መንገድ ይከተሉ ዘንድ ባለሙያዎች ይመክሩዎታል፡፡ ፑሽአፕ ደረትን ለማጠንከር እንኳን በራሱ ተመራጩ ስፖርት አለመሆኑን በማስመር፡፡ የደረት ስፖርትን በማከናወን ተጠቃሚ የሚሆኑ ሁለት አይነት ክፍሎች መሆናቸውን ነው ባለሙያዋ የሚያስቀምጡት፡፡ የመጀመሪያዎቹ ፋት ነክ የሆኑ ምግቦች ተጠቃሚዎች ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ አዲስ ገቢዎች የተባሉት ደግሞ በእንቅስቃሴው ውስጥ መሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ጀማሪዎች ናቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ማለትም ፋት ነክ ምግቦችን የሚጠቀሙ ሰዎች፣ በኬሚካል በመታገዝ ከእንቅስቃሴው በቶሎ ለማገገም አቅም የሚፈጥርላቸው ሲሆን፣ ቀጣዩን የደረት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ለማድረግ በተፈጥሯዊ መንገድ በደረት ግንባታ ላይ ከተሰማሩት በላይ ከፍተኛ ዕድል አላቸው፡፡

ሌሎቹ በዚህ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ተጠቃሚ የሚሆኑ ጀማሪዎች መሆናቸው ነው ጥናቱ የሚያመለክተው፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ወገኖች በምን አይነት ፍጥነት እንቅስቃሴ ማድረግ እንዳለባቸው የሚለዩበት ጊዜ ላይ ስለማይደርሱ መሆኑ ነው የተጠቀሰው፡፡

5. የደረት እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ጊዜና አቅምዎን በከፍተኛ መጠን ይጠቀሙ፡፡ በርካቶች በዚህ ረገድ ስኬታማ አይደሉም፡፡ በጊዜ ምክንያት እንቅስቃሴውን ከሌሎች የሰውነት አካላቸው ጋር በመቀላቀል አልያም በቂ እረፍት ላያደርጉ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ የቀኑን እንቅስቃሴ በ30 ደቂቃ ውስጥ ለማጠናቀቅ ይጣደፋሉ፡፡ ባለሙያዋ እንደሚሉት ታዲያ በደረት የተፈቀደውን እንቅሰቃሴ በከፍተኛ ትጋት በቀን ከ50-60 ደቂቃ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ትልቅ ደረትን በመገንባት እንቅስቃሴውን በኃይል እና በመጠን በየጊዜው ማሳደግ ይጠይቃል፡፡ በዚህ ሂደት ታዲያ ትከሻን ጨምሮ ሌሎች የሰውነት ክፍሎቻችንን የሚያሰሩ እንቅስቃሴዎችን እንዳይቀላቀሉ ይመከራሉ፡፡ በሁለቱም ወገን ያሉትን የደረት ክፍልዎ እኩል መንቀሳቀሳቸውን ፈጽመው አይዘንጉ ሚዛንዎን ያሳጣዎታል፡፡

6. የሚያነሱትን ክብደትና የጊዜ መጠን ይወስኑ፡፡ ከሳምንት ሳምንትም ከክብደት ለመሸጋገር ቢያንስ 5 ደቂቃ ይውሰዱ፡፡

7. ትከሻዎን ከጉዳት ይከላከሉ፤ ሰውነቱን በስፖርት የሚገነባ ሰው ትከሻውን ከአደጋ የመጠበቅ ያህል ወሳኝ ተግባር የለም፡፡ ለዚህ እንዲረዳም ትከሻን በምናምን መሸፈን ሁለት ጥቅም ይሰጣል፡፡ የመጀመሪያው ሰውነታችን ተረጋግቶ እንዲቆይ ማድረጉ ሲሆን፣ ሌላው ዝቅተኛ የጉዳት ተጋላጭነት እንዲኖረን ያደርጋል፡፡

8. በሚገባ ይመገቡ፡- እንቅስቃሴ ባደረጉበት ዕለት ብቻ ሳይሆን አምስቱን ቀናት በሙሉ፣ ከፍተኛ የፕሮቲን መጠን ያላቸውን ምግቦች መመገብ ያስፈልጋል ይላሉ ባለሙያዎቹ፡፡

9. ብዙ ውሃ መጠጣት፡- በሰውነቱ በቂ ውሃ ያለው በ19% ጥንካሬው እንደሚጨምር ታሳቢ ያድርጉ፡፡ ይሄ ጥንካሬ አለዎት ማለት ተጨማሪ ክብደቶችን በማንሳት ጡንቻዎትን የማጎልበት አቅም ይፈጥርልዎታል ማለት መሆኑን ልብ ይበሉ፡፡ ወደ ጂም እስኪሄዱ ውሃ ካልጠጡ፣ እርስዎ ጊዜዎን እያጠፉ ነው ተብለዋል፡፡ በስፖርት ማዕከሎች የውሃ ኮዳዎችን ተሸክመው እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሰዎች ያስገርሙናል ነው የሚሉት ባለሙያዎች፡፡ በበቂ ሁኔታ ውሃ በሰውነታችን ውስጥ መኖሩን ለማረጋገጥ፣ ከ15-30 ባሉት ደቂቃዎች ሽንት መሽት ከቻሉና ንፁህ ፈሳሽ ከሰውነትዎ መውጣቱን ማጤን በቂ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ እንቅስቃሴ ከማድረግዎ በፊት በቂ ውሃ መጠጣትዎን በፍፁም አይዘንጉ፡፡

10. እንቅስቃሴዎን ይመጥኑ፡- ግዙፍ ደረትን ለመገንባት በተከታታይነት በመሬት ላይ የደረት ስፖርት ማከናወን ያስፈልጋል፡፡ ይሄ እንቅስቃሴ በቀጣይ የምናደርገውን መጠን ምን ያህል መሆን እንደሚገባው የሚወስንልን ነው፡፡

11. በቂ እንቅልፍ ያግኙ፡- አላርም የሚጠቀሙ ከሆነ በቂ እንቅልፍ እንዳላገኙ ማሳያ ሊሆን ይችላል፡፡ ከእንቅስቃሴ በኋላ በቂ እንቅልፍ ማድረግ ለውጡን ለማፋጠን ይረዳዎታል እና በተቻለ መጠን በቂ እንቅልፍ ሊያገኙ የሚችሉበትን መንገድ ይምረጡ፡፡

12. የደረት ቅርፅ ተፈጥሯዊ ነው፡፡ በደረትና በደረትዎ መካከል ክፍተት መኖሩ የሚያስቡትን ግዙፍ ደረት ለመገንባት ይረዳዎታል፡፡ ይታደሉታል እንጂ እንዲሉ፣ በዚህ ረገድ በተፈጥሯዊ መንገድ ደረት የተቸራቸው ሰዎች፣ የሚያስቡትን ደረተ ሰፊነት በቀላሉ መላበስ ዕድል ይፈጥርላቸዋል፡፡

እነዚህ 12 ምክረ ሐሳቦች፣ ወንዶችን ወደ ልዩ ቀመር ሊያመጡ ከሚችሉ መንገዶች መካከል ዋነኞቹ ናቸው፡፡ በሚቀጥለው ሳምንት ለሴቶች የተለዩትን ነጥቦች የምናቀርብ ይሆናል፡፡

The post Sport: ወደ ልዩ የወንድነት ቀመር የሚያመጡዎት ነጥቦች፡- ግዙፉ ደረት መገንቢያ 10 ምስጢሮች appeared first on Zehabesha Amharic.

!ይቅናህ! –ከሥርጉተ ሥላሴ

$
0
0

18.04.2015 /ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ/

ከሥርጉተ ሥላሴ 02.023.2014 (ሲዊዘርላንድ - ዙሪክ)

ከሥርጉተ ሥላሴ 02.023.2014 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

„ምንም፡ እንኳን፡ በለስም፡ ባታፈራ፣ በወይን፡ ሐረግ፡ ፍሬ፡ ባይገኝ፣ የወይራ፡ ሥራ፡ ቢጓደል፣ እርሾችም፡ መብልን፡ ባይሰጡ፣ በጎች፡ ከበረቱ፡ ቢጠፉ፣ ላሞችም፡ በጋጡ፡ ውስጥ፡ ባይገኙ፣ እኔ፡ ግን፡ በእግዚአብሔር፡ ደስ፡ ይለኛል፣ በመዳህኒቴ፡ አምላክ፡ ሐሤት፡ አደርጋለሁ። ጌታ፡ እግዚአብሄር፡ ሃይሌ ነው፤“

/ትንቢተ – ዕንምባቆም ምዕራፍ 3 ቁጥር 17-19/

እንዴት ሰነበታችሁልኝ የኔዎቹ – ደህና ናችሁን? ትናንት ሲፈናቀል እጅግ ይከፋኛል። ትናንትን የገነባው፤ ዛሬን ያስገኘው የነገም አስኳል ሊሆን የሚችል ዕውነት ጥግ ሲያጣ ወይንም አትኩሮት ሲነፈገው ወይንም በቅጡ ማስተዳደር ሲሳነን – ያርመጠምጠኛል። ስንት ጊዜ ይማጥ ይሆን?

በፈተና ውስጥ አብዝተው ዋጋ የሚከፍሉ የምናፍቃቸውና የምሳሳላቸው ወገኖቼ ከእነሱ በከፋ ሁኔታ ያሉም እንደሉ ልብ ሊሉት ይገባል ባይ ነኝ፤ እኔው ሥርጉተ ሥላሴ። ከሁሉም እጅግ የከፋው ጎምዛዛ ገጠመኝ በሰው እጅ ቁጥጥር ሥር መሆን ነው። በሰው ቁጥጥር ሥርነት ክስ ደግሞ በስውርም በግልጽም ሊሆን ይችላል። በስለላ ወይንም በካቴና። „ለወንጀለኝነቱም“ ሎቶ ስብኃት ስለ ቃሉ፤ ሳቢያ ይፈለግለታል። በዘመነ ናዚ፤ የናዚን ፓሊሲ የተቃወሙ፤ የስድስት ሚሊዎንን አይሁዳዊ ህይወት ቀድመው ለመታደግ፤ ሀገራዊ ታሪካቻውንም ለማዳን ይተጉ የነበሩ „አሸባሪ“ ይባሉ ነበር። ለአዶልፍ ሂትለር እነኛ የሰብዕዊነት ደቀመዝሙሮች በአደባባይ „አሸባሪ“ ተብለው ተወገዘዋል፣ ፍዳ መከራቸውን አይተዋል፤ ደማቸውንም አፍሰዋል። በዘመነ አፓርታይድም የሰላም አባት የተከበሩ ኔልሰን ማንዴላም „አሸባሪ“ ይባሉ ነበር። በእኛም የሄሮድስ ራዕይ የፈበረከው ዘር የማክሰል ዘመቻዊ አፓርታይዳዊውን፤ ዘመነ ሱባኤ የተቃወሙ፣ የተሟገቱ „አሸባሪ ወንጀለኛ ናቸው“ ምንም እንኳን ለታደሉት ቀና ብሎ ለመናገር እውነት መድፈር የትውልድ ክብርና ጌጥ፤ ልዩ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ አስገኝ ኃይል፤ ልዩ አዲስ ቀለም ቢሆንም፤ ለእኛ ግን እነሱ የተከደኑ ሲሳዮቻችን፣ ታሪኮቻችን፣ ጀግኖቻችን ናቸው። የመንፈስ ሃብታት፤ ሽልማትም!

አብሶ ፋሽስት በነገሠበት ወቅት የነፃነት ቀማኛው አፈጻጸሙ ሴራማ፤ ሥሩም ትብትብ ነው። ስለዚህም በአንድም በሌላም መንገድ በፈተና አጥር ያሉ ወገኖች ከእነሱ እጅግ በባሰ ጥምዝዝ ገጠመኝ ላሉት፣ በፍም ድቅድቅ ውስጥ ለተማገዱት ደሞቻቸው ማሰብ ይገባቸዋል። ልሳናቸውን ወደ ህዝብ ሲልኩ ጥበብ ያስፈልጋቸዋል – ይመስለኛል። ለደራጎን ማመሳከሪያ – መረጋገጫ ገበር ከመሆን በእጅጉ መቆጠብ አለባቸው። እንዲሁም ቀጣይ አቅም ተስፋ አጥ እንዳይሆንም ከልባቸው ሆነው ሊመትሩት ይገባል። ተስፋ – ያውላል – ያሳድራል – ያኖራልና። ተስፋ የማይለቅበት የሩኽ ስንቅ ነው።

በሌላ በኩል ለአማንያን የመንገድ ምርጫ ጌታ መዳህኒት ፈጣሪ አምላክ ስለመሆኑም  „አለሙን፡ ሁሉን፡ ከፈጠረ፡ ከእግዚአብሄር፡ ከህጉ፡ ከሥርዓቱ፡ የወጣ፡ የለም፡ በሰማይ፡ የሚበር፡ ያሞራ፡ ፍለጋ፡ ቢሆን፡ ወደ፡ ወደደበት፡ መሄጃውን፡ እሱ፡ ያዛል።“ / መጽሐፈ መቃብያን ሣልሳ ምዕራፍ 9 ቁጥር 2/። „ … ያሞራ ፍለጋ ቢሆን ወደ ወደደበት መሄጃውን እሱ ያዛል“ ይላል አካል የሌለው የእግዚአብሄር ትጉኽ አገልጋይ ወንጌል፤ እንኳንስ የሰው ልጅ። የነፃነት ቀማኛው ቀንዶና ቁጭሎቹ እጅግ በበረከቱበት፤ ገደብ አልፎ የነፃነት ጥሰቱ አና ባለበት በዛሬው ጊዜ፤ እዳሪ ላይ በግፍ የወደቀ ነፍስ እልፍ በሆነበት ህማማተ – ዘመን፤ ባለቤት ያጣ ህዝብና አፈር – ለባዕቱ በባዕድነት የተገፋ ህሊና የሚችለውን ሁሉ፤ በቻለው መንገድ እንደምርጫው እንዲከውን የፈቀደለት አምላኩ ብቻ ነው። ስለሆነም ግፊያ አያስፈልግም።

ከእንሰሳ በታች ክብሩ ተገፎ በዬሄደበት እዬታደነ የሚቃጠለው ሥጋና ደም ጪስ እረፍት የነሳው ወገን በአሻው መንገድ የድርሻውን ሊወጣ መሰናዳቱ ሆነ፤ ውጤቱን በአግባቡ ቢተረጎም መልካም ነው። „ነፍሴን ለሀገሬና ለህዝቤ ክብር ብሎ ለመማገድ መቁረጥ“ በራሱ የድል ዋዜማ ነው። ለአንድ ነፃነትን ፈላጊ ድርጅት ወይንም ግለሰብ ወይንም ማህበር ሊሆን ይችላል፤ የነፃነት ፍቅረኛነቱን ከእሱ ለዬት ያለ የነፃነትን መገኛ አማራጭ መንፈስን ቢያንስ በህሊናው ጥበቃ የማደረግ አቅሙ ባለቤቱን ይለካዋል። ስለምንስ ምስጋናው ቀርቶበት፤ ሞትን ቆርጦ ለተሸከመ ሰላሙ ይተዋካል? ነፃነቱን ይቃማል? አይገባኝም። እንዲገባኝም – አልፈልግም።

ጤፍ እንጀራ በእርጎ እኔ መች ጠልቼ፤ ? ? ?

ሲበሉ ለማዬት – ፈቃድ ተነስቼ፤ ? ? ?

ጉሮሮ ለማርጠብ እንዲህም  – ተሟሙቼ፤ ? ? ?

በእቃ ተገምቼ – እንደ ዕቃም ታይቼ

ቢቸግረኝ እንጂ፤ —- መች ክብር ጠልቼ!

ቢከፋኝ ነው እንጂ፣ – ዱሩን ተመኝቼ

መጠለያ ከፈን አፈሩን በልቼ

ቅንቅን በቋጠሮ – ዕንባነን አውግቼ።

የነፃነት ፍለጋ መንገድ ሎተሪ አይደለም። ደግሞም ቀኑ ቢረዝምም ሀሰትን ተስፋ ያለደረገ መንፈስ መጨረሻው አሸናፊ ነው። ውዶቼ – የኔዎቹ – ይህን ግጥም ስጸፈው መንፈሴን እያመመኝ መሆኑን ጨምሬ እገልጻለሁ። ህመሙ ሥም የለሽ ነው። ምክንያቱም፤ እንዴት ያደርግሻል? ብባል መግለጽ እችል ዘንድ አልተሰናዳሁምና። ብልህነት ብልጫ ነው። ብልጫው ደግሞ ብርቅነትን – ያሰነብታል። ብርቅነትን ለማዝለቅ ለብዙኃኑ መንፈስ ፅኑ ጠባቂና ጠንቃቃ መሆንን ይጠይቃል። የመንፈስ ሃብት ዕትብታዊ ትቅቅፉ ረቂቅ ነው። አንዱን ሲነኩት ሌላው ይነቃነቃል ወይንም ይናጋል። መስተጋብራዊ ውህደቱ ሰውኛ አይደለም እና። እንደ ተለመደው ቃናው ሆነ ምቱ ሁልጊዜ በአንድ ማስኬድ አይቻልም። ድምጽ ላይ ሲወጣና በልክ ሲጓዝ ወይንም ጥልቀትን ሲመርጥ የሙዚቃ ባህሬ ብቻ ሳይሆን ዓይነቱም ሆነ መደቡ ይለወጣል። ባለሮኩ እንደ ባለሀገረሰቡ፤ ባለሀገረሰቡ እንደ ፖፑ፤ ባለፖፑም እንደ ቴክኖ ወዘተ … አያስኬዱትም። ፍቅር አብሶ የህዝብ ፍቅር ጥሩ አስተዳዳሪነትን ይሻል። በስተቀር – ይፈሳል። ለማንኛውም በዓይኔ ዞር የምትሉት እትብቶቼ ውስጤ ይሄውላችሁ –

!ይቅናህ!“

*

ከሆንልህ – እልል ልበልልህ።

ከታሳካልህ – ሆ! ብዬ ማጫ ልሁንልህ።

ግን ለባለዛገ ጆሮ አታውስኝ

አትንቀሰኝ – አትውቀሰኝ

የወጨፎ ማዕትህ እኮ – በላኝ

ተለተለኝ፤

እንደ ተመቸህ – እባክህን አትሰልቀኝ?

ይበቃኛል! የባለጊዜ፤ – የጎጠኛ አባዜ

የዘመንተኛ ጃርተ – ሟርት፤  የለዛዜ።

አንተም ባሻህ፤ እኔም ባሻኝ

የአቅሜን መሻቴን እባክህን? – አክብርልኝ።

አይዋ! የኔው በሻ – አታድርገኝ ሆደባሻ

እንደ ልቤ ሸኜኝ፤ እንደ ልብህ ልሸኝህ።

ግን! አዎን! ግን – አትውቃኝ

አትሰቅዘኝ፤

ዬአፓርታይዱ ላይበቃኝ! አንተ ተደምረህ – አታጣውረኝ፣

አታ—-ሳ—-ጣኝ። አታ —- ሥ —- ጣኝ።

አ-ት-ቀ-ረ-ጣ-ጥ-ፈ-ኝ

በመስቃ  አ-ት-ሰ-ነ-ጣ-ጥ-ቀ-ኝ

አትሰልቀኝ፣

አታዋክበኝ ——አትበጣጥሰኝ።

ህም! —- የደም አንባር አይደለሁ፤

መውጫ ባጣ አማራጩን ለተስፋችን ተመኜሁ …..

ዱር ገደሉን ለወላችን – ሞረሽ አልሁ፤

እንጅ፤ እኔማ! ቢያቀማጥሉኝ መቼ ጠላሁ?!

እኮ አንተስ!!? አንተስ፤ ብትሆን ሰኞኛ

ሰውኛ ሁነህ ብትቦጭቀኝ – አይቀርብኝ – ድርሻዬ ይቀልልኝ

ኃጢያቴ – ይሠርይልኝ፤

ብቻ አዎን ብቻ፤ ታናሼዋ – ዳኛው ህዝብ ነው ይፋረደኝ።

እኔ ከሆንኩኝ ጥፋተኛ … ?

…. የማገዶ – አስቀማኛ?

የትውልድ – ቀበኛ …..?

—- የቀንበጥ – እግረኛ?

የደም ጥማተኛ ….?

…. የበቀል – ጉሮሮኛ?

ሀገራዊ – በደለኛ …..?

~~~~~~አድሎኛ~~~~~~~?

እ! ተጠያቂ ለዛውም – ዕንቡጤን አሳልፌ አሰጪ ለዱለኛ —-?

? ? ? ? —-

ለዘር – ብለኛ?

እም! –

የራስ – ህመም -

እማዳግም?

ይሁንልህ ብቻ – አዎን! ብቻ ይፋረደኝ – ዘመን

ይዘምዝመኝ – ይፍተለኝ

እንዳሻው – ያፍተልትለኝ።

ምነው እግረ ተከሉ ታናሼ? ክንድዬ – ታሪክንም ቢሆን አሳርፈው -

አትወርፈው!

ምን ባጣፋ እንዲህ ታቁስለው?

ቁም – ተቀመጥ፤ አትበለው?

አታሳቅለው -

ይበቃዋል – የእነሱ

የነማተበቢሱ።

ለቀን ያደረሰን እሱው ነው ———–በቅኔ ቤት ለካው፤

ባለ አፈር፤ ባለ ቋንቋ፤ ባለማተብ፤ ባለመቀነት – ጥቁር ንጡር አልማዝ እሱውልህ

አስላው – በሚያበለው – ፤

ውልህ።

የአፍሪካ ሰንደቅ፣ የጥቁር ዓርማ። ባርነትን ሰንጥቅ፣ – ድንቅ – እፁብ ፍልቅ፤

እንደ እንሰሳ መሬት ላይ ያላስጎተተኝ/ተህ/

ቀና አድርጎ ያናገረኝ/ህ/ — የትናንቱ የ3000 ከዚህም በላይ ውለኛ። የእናት ያባትህ – ርስትህ – ዋጋ አስራትህ፤

የራስህ ——

ትርሲትህ፤

ቅርስህ።

አያ አንቫዬ! ይልቅ ሥራህን – ሥራ ———

ሥራህ በርቶ ዴሞክራሲን – እስኪያበራ፤ – እስኪናገር – እስኪያወራ ከታሪክ ጋራ

ድምፅ መራሽ ሸንጎ እስክታለማ ——

እስክትሁን – ጉልት ማማ።

ትእግስት ሸምት ከእዮብ ጎራ፤

ከአባ መሆን ጎመራ

ከቅድስና አውራ።

ተወኝ! አልኩኝ – ይበቃኛል የእነሱ

እባክህን! አትነስተኝ ቀልቤ ሆኗል ስሱ፤

የእናት ሀገር ፍቅር ትዝታ – ስስቱ

የአደራ ጥሪት ትሩፋቱ

ሳልመልሰው ገድላዊ ታምራቱ

አቫዝቶኛል ቀን መግፋቱ።

እኮ!

እኮ! ከእኔ ምን አለህ?! – የእናቴ ልጅ በፈቀድከው ባሰኘህ መጪ በል …..

ከሳቱ ላይ እያለህ – አንተም ተረመጥኽ

እያንገበገቡህ – እዬወቁኽ

ከ—–ዘመንተኛ ልቀህ አትዘልዝለኝ – አትዘቅዝቀኝ፤

አትጎልጉለኝ – አትፈርፍረኝ።

ቁጥሩስ ቢሆን ጋሻዬ፤  እኩል – ለእኩል

እኔም አንተም ዬባለ24 ክናድ ባለኩል

የዕንባ – ኩልል።

ልንተያዬ ቀናት ሲያፈጥ——–

ምነው እንዲህ ቸኮልክ – ለማፋጠጥ!?

ይዘኸዋል – ታዬዋለህ

ብቻ ከእኔ ወረድ በል።

አሪወሱ – ባለ ጎራዴ

ተስፋ በቀረመት ጎራርዴ

አለልህ ቋሰኛው – ሸለሸሉ ጉርዴ።

እኔን ለቀቀ! እሱን ጠበቅ!

ጉባኤውን በድል ጥልቅ!

ዳኝነቱን ለህሊና አጥልቅ።

ወልደህ እዬው እንዳልልህ …

አንተም ህዋሴ ሆንክና፤ ምርቃቴን ላኩልህ።

እኔ እንዳተ አይደለሁም። ክብሬ – መንፈሴ – ጥንዴ – አልኩህ

የእኔ ጌጤ ብዬ፤ ውስጤን መርቄ ሸለምኩህ።

ሥጦታነትህን – በውስጥነት አወጅኩልህ

መንገድህን ይቅናህ! ይቅናልኝ፤ ድል ያቅናልኝም – አልኩህ!

እደግልን – ዘለግ ይበል ድልህ

አሁንም እልሃለሁ – በአጭሩ ከደመደመክ – ይሳካልህ~!

አርጎትነው አዶናይ! … እሰይ … እሰይ … ይሁንልን – ይሁንልህ፣

የእመቤቴም ጥበቃዋ አይለይህ፤

መቋጫውን ሐሤትማ – አማንዬ ያድርግልህ

አንደ ልብህ – አንድያዋ – ያሳማማልህ።

ሥጦታ – ለቁስለኛ – ከቁስለኛ።

© Seregute Selassie ሥርጉተ ሥላሴ –  08.04.2015 ሲዊዘርላንድ – ቪንተርቱር።

የኔዎቹ መሸቢያ ሰንበት ተመኝቼ የቤት ሥራ እንሆ – ብትህትና፤ ይህቺን ድግም – ድግምግም አድርጋችሁ ብታነቧት  ትፈወሳላችሁ። „ይህቺ ሐገር ሚስጢር ናት“ ከጸሐፊ ከተማ ዋቅጅራ – እግዚአብሄር ይስጥልኝ። በህሊናችን ሰሌዳ ዓምድ የሆነ ወርቅ አገላለጽ ከጭብጥ ተነስቶ በዕውነት አምክንዮ – የሰከነ። እጅ ይባርክ! http://www.zehabesha.com/amharic/ ውድ ዘሃበሻ – ውድድድ – ኑሩልኝ!

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር!

ኢትዮጵያ አላዛር ናት!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

The post !ይቅናህ! – ከሥርጉተ ሥላሴ appeared first on Zehabesha Amharic.

ወያኔ እና የቅድመ-ምርጫ ግምገማው- ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት

$
0
0
  • ወያኔ የአምስት ዓመቱ «የዕድገት እና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ» እንዲሁም የዐባይ ግድብ ግንባታ እንዳልተሳካለት አመነ፣
  • በመጭው ምርጫም የሚያሰጋኝ የድርጅትም ሆነ የግለሰብም ተወዳዳዳሪ የለኝም አለ።

Moreshየትግሬ-ወያኔ መራሹ ዘረኛ አገር እና ትውልድ አጥፊ ቡድን፣ መጭው የይስሙላ ምርጫ ሊያስከትል የሚችለውን ሕዝባዊ ቁጣ እና  እምቢተኝነት በከፍተኛ ደረጃ በመፍራት፣ ሊነሣ የሚችለውን ሕዝባዊ አመፅ በወያኔ ፍላጎት ሥር ለማዋል እንዲቻል፣ አባላቱን በመከፋፈል፣ ሰሞኑን በከፍተኛ ደረጃ የተያዘ ጥብቅ ሚሥጢራዊ ግምገማ እና ውይይት ማድረጉን የታመኑ የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ውስጥ-ዐወቅ የመረጃ ምንጮች አረጋግጠዋል። የሕወሓት/ኢሕአዴግ አባል በሆኑ እና ለወያኔ ታማኝ የሆኑ የየድርጅቶቹ አባሎች ተሣታፊ የሆኑበት ለበርካታ ቀኖች በተከታታይ ግምገማ እና ውይይት የተደረገባቸው ጉዳዮች፦

አንደኛ ፦አቶ ኃይለማርያም ደሣለኝ በኃላፊነቱ ይቀጥል ወይስ ይነሣ?

ሁለተኛ፦የትግሬ የበላይነት አለ? ወይስ የለም?

ሦሥተኛ፦የአምስት ዓመቱ «የዕድገት እና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ»፣ እንዲሁም የዐባይ ግድብ ግንባታ በታቀደው መልኩ ያለመከናወናቸው መሠረታዊ ችግሮች ምንድን ናቸው?

አራተኛ፦ በ2007 ዓ.ም. ምርጫ ጠንካራ ተቃዋሚዎች አሉ ወይ? ካሉስ እነማን ናቸው?

የሚሉት እንደሆኑ ታማኝ እና ሁነኛ የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት የውስጥ-አዋቂ ምንጮች አረጋግጠዋል።

በርዕሰ ጉዳዮቹ ላይ በተደረገው ግምገማ እና ውይይት ከሚከተሉት ውሣኔዎችና ድምዳሜዎች ላይ መደረሱን ምንጮች አስረድተዋል። አቶ ኃይለማርያም በያዘው የጠቅላይ ሚኒስቴርነት ኃላፊነት ይቀጥል? ወይስ አይቀጥል፣ በሚለው ጉዳይ ላይ የወያኔ ቡድን አንድ ቁርጥ ያለ አቋም ላይ ለመድረስ እንዳልቻለ ታውቋል። ከሕወሓት ውጭ ያሉት እና «የኢሕአዴግ አባል ድርጅቶች» የሚባሉት አባሎች፣ «ኃይለማርያም ወያኔ ከሚሰጠው መመሪያ ውጭ የማይንቀሳቀስ በመሆኑ በያዘው ቦታ ቢቀጥል የሚያመጣው ችግር የሌለ ስለሆነ ይቀጥል» ሲሉ፣ የወያኔ አባላት ከሆኑት የተወሰኑ ትግሬዎችም «እስካሁን እኛ ያልነውን ብቻ ሣይሆን፣ ያሰብነውን እና ልንሠራ የምንፈልገውን ቀድሞ የሚናገርልን ስለሆነ በያዘው ቦታ መቀጠሉ ለወያኔ ዓላማ መሳካት ያግዛል እንጂ አይጎዳም» ሲሉ መደመጣቸው ታውቋል።

በሌላ በኩል «አክራሪ» እና «ለምን ከወሣኝ የሥልጣን ቦታ ላይ ትግሬ ይጠፋል? እኛ ሞተን እና ቆስለን ባስገኘነው ሥልጣን የሌላ ነገድ አባል የሆነ እና በትግሉም ወቅት ምንም ዓይነት አስተዋጽዖ ያላደረገ ሰው፣ በመለስ ዜናዊ ብቸኛ ውሣኔ ለዚህ ቦታ የበቃ ሰው፣ ለተከታዮቹ አምስት ዓመታት በሥልጣን ላይ መቆየት የለበትም» በማለት ኃለማርያም በሌላ ትግሬ እንዲተካ የከረረ አቋም መያዛቸው መስተዋሉን የሞረሽ ምንጮች አስረድተዋል። «ኃይለማርያም መነሣት አለበት» የሚሉት የወያኔ አባሎች የሚያቀርቡት የመከራከሪያ ነጥብ፣ «ኃይለማርያም ከወያኔ ፍላጎት ያፈነገጠ ጠባይ ባይታይበትም፣ የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ ለእርሱ የሚደርስ በመሆኑ፣ መረጃዎች ለወያኔ የሚደርሱት በሁለተኛ ደረጃ ስለሆነ፣ ፈጣን ውሣኔዎችን ለመስጠት ተቸግረናል። ለዓላማችን መሣካትና በፈለግነው አቅጣጫ ለመጓዝ የጠቅላይ ሚኒስቴርነቱ ቦታ በትግሬ መያዝ አለበት» የሚል መሆኑ ታውቋል። ኃይለማርያም ደሣለኝ መነሳት አለበት የሚለው ቡድን በተጨማሪ መከራከሪያነት የሚያነሳው ጭብጥ አለ። ይኸውም፦ «ለአምስት ዓመቱ የዕድገት እና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ እና ለዐባይ ግድብ ግንባታ መክሸፍ ዋነኛ ምክንያቱ የአመራር ድክመት፣ የውጭ ፖሊሲያችን ውድቀት» መሆኑ መወሳቱ እና «መለስ ቢሆን ወይም ሌላ ትግሬ አመራሩን ቢይዝ ኖሮ ይህ ውድቀት አይከተልም ነበር። ኃይለማርያም ፈጥኖ የመወሰን ብቻ ሣይሆን፣ በራስ የመተማመን ችግር ስላለበት በእርሱ አመራር ወደ ግባችን መድረስ አንችልም።» ከሚል ድምዳሜ መድረሳቸውን ያስረዳሉ። ይህ የተከፋፈለ አመለካከት «ኃይለማርያም ይቀጥል? ወይስ በሌላ ይተካ?» ለሚለው ጥያቄ ቁርጥ ያለ መልስ ላይ አለመደረሱን ምንጮቻችን አስታውቀዋል።

በዚህም ይመስላል፣ ወያኔ የመጭውን ምርጫ ውጤት ተከትሎ ሊቀሰቀስ ለሚችል ሕዝባዊ አመፅ፣ ቀጥቅጦ እና ጨፍልቆ የወያኔን የበላይነት ለማረጋገጥ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በ«ሕገመንግሥቱ የተሰጡትን ሥልጣኖች» በመሻር፣ ጊዜያዊ አዋጅ ከማወጅ አንስቶ፣ የአገሪቱን የመከላከያ፣ የደህንነት እና የፖሊስ ኃይል በበላይነት የሚመራ እና የሚቆጣጠር ኮሚቴ ፈጥሯል። የኮሚቴው ሰብሳቢም ጨካኙ እና ፈሪው ዐባይ ፀሐዬ እንዲሆን ተደርጓል። ይህን ውሣኔ ከላይ «ኃይለማርያም ይነሳ? ወይስ ይቀጥል?» ለሚለው ጥያቄ መነሳት አለበት የሚሉት ወገኖች አቋም ከወዲሁ አንድ እርምጃ ወደፊት የተራመደ እና ኃይለማርያም በዐባይ ፀሐዬ የተተካ መሆኑን ያሳያል። ምክንያቱም ኃይለማርያም ለይስሙላም ቢሆን በወረቀት ላይ የተሰጡትን ወሣኝ የሆኑትን ሥልጣኖቹን አጥቷልና!

«የትግራይ የበላይነት አለ? ወይስ የለም?» ለሚለው የመገማገሚያ ነጥብ፣ እጅግ በርካታ ሰዎች «የትግራይ የበላይነት አለ። በሁሉም የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ እና የኢኮኖሚ ዘርፎች፣ ከትንሽ እስከ ትልቅ በትግሬዎች የተያዙ ናቸው» ሲሉ፣ የተወሰኑት ደግሞ፦ «የትግሬ የበላይነት የለም» እንዳሉ የመረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል። በየትኛውም ደረጃ የየውይይቱ መሪዎች ትግሬ ካልጠፋ በስተቀር ሁሉም ትግሬዎች ናቸው። እነዚህ አገማጋሚዎች «የትግሬ የበላይነት አለ» ሲሉ ኃሣባቸውን የገለጹትን፥ «የትግሬ የበላይነት አለ ስትሉ የበላይነቱ በምን፣ በምን እንደሚገለፅ አስረዱ» በማለት ተገምጋሚዎችን አፋጥጠው መያዛቸው ታውቋል። ተገምጋሚዎቹም ለተጠየቁት ጥያቄ ሲመልሱ፦ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ መስኮች ወሣኝ ቦታዎች ብቻ ሳይሆኑ ጥቃቅን ቦታዎች ሳይቀሩ በትግሬዎች መያዙ፤ ትግራይ ከሌሎች ክልሎች ተነጥላ እንድትበለጽግ መደረጉ፤ ከፍተኛ የሆነ የትምህርት፤ የጤና፣ የመገናኛ፣ እና የኢንዱስትሪ ግንባታዎች በትግራይ መሠራታቸው፤ የቀረው ቀርቶ ትግርኛ መናገር የማያስፈትሽ እና የማያስጠይቅ እንደሆነ ተጨማጭ ማስረጃዎችን በማቅረብ መልስ እንደሰጡ ታውቋል። ለተሰጡት መልሶች አወያዮቹ «ይህማ የግንቦት 7 እና የኢሣት ፕሮፓጋንዳ ነው። ትግሬን የሚጠሉ ሰዎች አቋም ነው። ጥቅማቸው የተነካባቸው የቀድሞው ሥርዓት ናፋቂዎች የሚያራግቡት ፖለቲካ ነው» በማለት እንዳጣጣሉት ለማወቅ ተችሏል። በሚያስገርም ሁኔታ «የትግሬ የበላይነት የለም» ያሉትን ደግሞ «እናንተ አድርባዮች ናችሁ! ወላዋዮች እና አስመሳዮች ናችሁ። ግምገማው ተገቢውን ውጤት እንዳያስገኝ ያሰባችሁ ናችሁ» በማለት የዘለፉዋቸው እንደሆነ ሲታወቅ፣ በዚህ የመገማገሚያ ርዕስ አንድ ዓይነት አቋም ላይ ሳይደረስ፣ አወያዮቹ እንደተለመደው የተሰጡትን ኃሣቦች በማጣጣል ውይይቱ መደምደሙ ታውቋል።

በሦሥተኛ ደረጃ የመገማገሚያ ርዕስ በነበረው በተደረገው ግምገማ እና ምዘና፥ «የአምስት ዓመቱ የዕድገት እና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ እንዲሁም የዐባይ ግድብ በታሰበው መልኩ አለመከናወኑ ብቻ ሳይሆን፣ አጠቃላይ ውድቀት እንደሆነ» በሙሉ ድምፅ መስማማታቸውን ምንጮቻችን አረጋግጠዋል። ለዕቅዶቹ አለመፈጸም መሠረታዊ ምክንያቶች ሆነው የተጠቀሱት፦ «ከአበዳሪ እና ለጋሽ መንግሥታት እና ድርጅቶች ይገኙ የነበሩት ዕርዳታዎች እና ብድሮች መቋረጥ፣ ለዕቅዶቹ ተፈጻሚነት የሚያስፈልጉት ግብዓቶች አብዛኛዎቹ ከውጭ መሆን እና ይህን ማግኘት አለመቻሉ» እንደነበረ ሲጠቀሱ፣ «ይህ ደግሞ የውጭ ፖሊሲያችን ውድቀት መሆኑ፣ የፖሊሲው ውድቀት ደግሞ ብቃት ያለው እንደመለስ ያለ መሪ አለመኖሩ» እንደሆነ በስፋት መገለጹን የውስጥ-ዐወቅ የመረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል። በመሠረቱ መለስ ዜናዊ ይህንን የቅዠት ዕቅድ ሲያወጣ፣ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት የሚያስፈልጉት አግባብ ያላቸውን ፖሊሲዎች እንዳልቀረፀ ይታወቃል። ከዚያም በላይ የአንድ አገር የኢኮኖሚ ዕድገት በውጭ ዕርዳታ እና ብድር በሚገኝ መዋዕለ-ንዋይ ብቻ ይከናወናል ብለው የሚያስቡ ገዢዎች፣ ከመነሻውም ያለባቸውን የአመራር ድክመት የሚያሣይ ነው። ስለዚህ ብዙ የተደሰኮረለት «የአምስት ዓመቱ የዕድገት እና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ» ውጤቱ ዜሮ ቢሆን ቀድሞውንም የሚጠበቅ ነው።

የ2007 ዓ.ም. ምርጫን በተመለከተ በተደረጉ ግምገማዎች እና ምዘናዎች፣ ሕወሓት/ኢሕአዴግን የሚያሰጉ፣  በሕዝቡ ተቀባይነት ያላቸው ድርጅቶችም ሆኑ ግለሰቦች እንደሌሉ በገምጋሚዎቹ እይታ ሙሉ እምነትና ስምምነት መደረሱ ታውቋል። በሌላ በኩል «ብቻቸውን ለምርጫ ቀርበው ለምን ምርጫ ይላሉ?» ለሚሉ ወገኖች አፍ ማዘጊያ፣ እንዲሁም  እንዳለፈው ምርጫ «በ99ነጥብ6 አሸነፍን» ላለማለት፣ «በዓላማ ከእኛ ጋር የሚስማሙትን፣ በአፈጻጸም የሚለዩትን በመድረክ ሥር ከተሰባሰቡት ሰዎች በድርጅት ስም ሳይሆን፣ በግለሰብ ደረጃ ተመርጠው የፓርላማ ወንበር የሚያገኙበት ሥልት እንዲመቻች» በማለት መስማማታቸው ተረጋግጧል።  ይህም ለታማኝ ተቃዋሚዎቻቸው ለእነ ፕሮፌሠር በየነ ጴጥሮስ፣ ለዶክተር መረራ ጉዲና፣ ለአቶ ገብሩ አሥራት ዓይነቶች በር የተከፈተላቸው እንደሆነ ይጠቁማል። «ይህን ሁላ አድርገንም ምርጫውን እኛ አሸነፍን ብንል ሕዝቡ ሊቀበለን ስለማይችል፣ ይህን ተከትሎ ለሚፈጠር አመፅ አስፈላጊውን የኃይል ርምጃ የሚወስድ በቂ ዝግጅት እንዲደረግ» የሚል ውሣኔ አሣልፈዋል። ይህም ቀደም ሲል ጀምሮ የታሰበበት እንደሆነ ታውቋል። ስለሆነም ከይስሙላው ጠቅላይ ሚኒስትር ከአቶ ኃይለማርያም ደሣለኝ ሥልጣን የተረከበው በዐባይ ፀሐዬ የሚመራው ኮሚቴ ዐቢይ ተግባር፣ ሕዝባዊ አመጽን መስበር እንደሆነ የኮሚቴው ዓላማና የግምገማው ውጤት ያሳያል። ለዚሁ ተግባር ሲባልም በከተሞች የተጠናከረ የስለላ እና የመቺ ኃይል ቡድኖች ተደራጅተው በመንቀሳቀስ ላይ እንደሆኑ ታውቋል። በገጠር የገበሬ ማኅበራት በእያንዳንዱ ምርጫው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ ከፍተኛ ገንዘብ የሚከፈላቸው ከአንድ መቶ እስከ መቶ ስልሳ የሚሆኑ አፋኝ ቡድኖች አባሎች መመደባቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል። የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ በየአምሥት ዓመቱ የይስሙላ የምርጫ ድራማ እንደሚያዘጋጅ እና ውጤቱም ሁልጊዜ በትራጄዲ እንደሚደመደም ይታወቃል።

The post ወያኔ እና የቅድመ-ምርጫ ግምገማው- ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት appeared first on Zehabesha Amharic.


የሳይንቲስቱ ልጅ ጥያቄ –ከዳንኤል ክብረት (ዲ/ን)

$
0
0

ባለፈው እሑድ፣ የትንሣኤ ዕለትማልዳ ነው ከዕንቅልፏ የተነሣቺው፡፡ እናቷ ቤተ ክርስቲያን አድራ፣ አባቷ ደግሞ ሌሊት ከውጭ ሀገር ገብቶ ደክሟቸው እንደተኙ አልተነሡም፡፡እርሷም በጠዋት የተነሣቺው ጓደኛዋ አደራ ስላለቻት ነው፡፡ ‹‹የቴሌቭዥን የትንሣኤ ፕሮግራም የተቀረጸው እኛ ቤት ነው›› ብላ አጓጉታታለቺ፡፡የተነሣቺው ጓደኛዋን በቴሌቭዥን ለማየት ስትል ነው፡፡ ደግሞ ‹ዘፈን ምናምን አቅርቤያለሁ› ብላታለቺ፡፡ የጓደኛዋ አባት ‹ፍቅርእዚህም እዚያም›፣ ‹ትሄጅብኛለሽ› እና ‹ፍቅር በኪችን ውስጥ› የተሰኙ ሦስት አስቂኝ የፍቅር ፊልሞች ላይ የሠራ ‹ታዋቂ አርቲስት›ነው፡፡ ጓደኛዋ እንደነገረቻት ከሆነ የበዓሉ ፕሮግራም እነርሱ ቤት ሲቀረጽ የቀረ አርቲስት የለም፡፡ በዓሉ ራሱ ሕዝቡን ሊያዝናናስለማይችል ‹ዘና እንዲያደርጉት› ተብሎ ቀልደኞቹ ሁሉ እነርሱ ቤት መጥተው ነበር፡፡
daniel
ከቀረፃው ማግሥት ጓደኛዋ ትምህርትቤት ስትመጣ የታዋቂ አርቲስቶችን ፊርማ በየደብተሯ ሰብስባ መጥታ ጓደኞቿን ሁሉ ስታስቀናቸው ነበር፡፡ በርግጥ ክፍል ውስጥ እርሷናጓደኞቿ ትምህርታቸውን ረስተው የአርቲስቶችን ፊርማ ሲያደንቁ ያዩዋቸው መምህራቸው እንደ መገሰጽ ቢያደርጉም፣ እንደመስማት ያላቸውተማሪ ግን አልነበረም፡፡ ምክንያቱም እርሳቸው ታዋቂ አይደሉማ፡፡ ደግሞ መምህር ከመቼ ወዲህ ነው ታዋቂ የሚሆነው፡፡ ይኼው ስንቱአርብቶ አደርና አርሶ አደር ሲሸለም መምህር መቼ ተሸልሞ ያውቃል፡፡ በተለይ ደግሞ ብዙዎችን ተማሪዎች ያናደዳቸው ‹‹የዘፈነም፣የተወነም፣ ፊልም የሠራም፣ ማስታወቂያ የሠራም አርቲስት አይባልም›› ያሉት ነገር ነው፡፡ ‹‹አርቲስት የሚለው ስም ለሰዓሊዎች የሚሰጥስም ነው፡፡ ያውም ስካልፕቸርና ፔይንቲንግ ለሚሠሩት ብቻ፡፡ እርሱምቢሆን እንደ ደጃዝማችና ግራ አዝማች ማዕረግ ሳይሆን የሞያ መጠሪያ ነው፡፡ እስኪ አሁን አርቲስት ማይክል ጃክሰን፣ አርቲስት ቢዮንሴሲባል ሰምታችሁ ታውቃላችሁ? ሰው ማዕረግ የሚያበዛው ስሙ ብቻውን ለመቆም ዐቅም ስለሚያጣ ነው፡፡ እስኪ ተመልከቱ፡፡ ዳቪንቼ፣ ሼክስፒር፣ሞዛርት፣ ፒካሶ የሚለው ስምኮ ብቻውን የሚቆም ነው፡፡ ዕዝል ቅጽል አያስፈልገውም፡፡›› ያሉትን ነገር ተማሪዎቻቸው ‹‹እርሳቸውከቴሌቭዥን ሊበልጡ ነው እንዴ›› ብለው ሙድ ያዙባቸው፡፡

ለነገሩ እርሳቸውም አብዝተውታል፡፡‹አርሶ አደርና አርብቶ አደር፣ ሠልጣኝና የትራፊክ ፖሊስ፣ ታራሚና ፍርደኛ፣ ጋዜጠኛና ጎዳና ተዳዳሪ ማዕረግ ሆነው ከስም በፊትበሚቀጸሉባት ሀገር ‹አርቲስት› ማዕረግ አይደለም ብለው ተማሪን ማሸበር በአሸባሪነት የሚያስከስስ እንዳይሆን ያሰጋል፡፡ እንዲያውምኢቲቪ ቢሰማቸው ‹በአሸባሪነት ሊያስከስስ ይገባል ሲሉ አንዳንድ የሕግ ምሁራን አስገነዘቡ› ብሎ ለዜና ጥብስ ያውላቸው ነበር፡፡
እርሷ ሶፋ ወንበር ላይ ተቀምጣይኼንን ሁሉ ስታስብ ጓደኛዋ በቴሌ ቭዥን ዘገየች፡፡ እስኪጀመር ድረስ ያቺ የ12 ዓመት የሰባተኛ ክፍል ተማሪ ማሰቧን ቀጠለች፡፡‹‹ቆይ ግን አባዬ ምንድን ነው? አንድም ቀንኮ በቴሌቭዥን ታይቶ አያውቅም፡፡ ይኼው ኤልዳና እንኳን ስንት ጊዜ በቲቪ ልትታዪ ነው፡፡አባዬ ግን ዶክተር ምናምን ከሚሆን አርቲስት ቢሆን ነበር ጥሩ፡፡ እርሱ ዶክተር ሆኖ ምንም አልጠቀመንም፡፡ አንዴ አሜሪካ አንዴጃፓን፣ አንዴ ጀርመን ለወርክ ሾፕ መሮጥ ብቻ ነው፡፡ በርግጥ የኤልዳናም አባት ውጭ ይኼዳል፡፡ ግን እርሱ ሲሄድም ሲመጣም በሚዲያይነገርለታል፡፡ ሊሄድ ነው፣ እየሄደ ነው፣ ሊደርስ ነው፣ ደረሰ ይባልለታል፡፡ የኔን አባት መሄድና መምጣት ግን እኛና የኢትዮጵያአየር መንገድ ብቻ ነን የምናውቀው፡፡

ደግሞ የኤልዳና አባት ውጭ ሲሄድሰው ይከበዋል፣ ጉርድ ቀሚስ ያደረጉ ሴቶች፣ ቁጥርጥር የተሠሩ ወንዶች፣ አጅበውት ፎቶ ይነሣሉ፡፡ የኔ አባት ግን ፎቶዎቹን ሁሉሳይ ወይ ከራሰ በራ ሰው ጋር ወይ ድክምክም ካሉ ሴቶች ጋር ነው የሚነሣው፡፡ ደግሞኮ የኤልዳና አባት ሁልጊዜ የአበባ ጉንጉን ሲቀበልነው የሚታየው፡፡ የኔ አባት ግን ሯጭ ይመስል ሜዳልያ ሲቀበል ነው የምናየው፡፡ ኤልዳና ቪዲዮውን በስልኳ ስታሳየን ሰው ሁሉ ኡኡእያለ አዳራሽ ውስጥ ለአባቷ ይጨፍርለታል፡፡ የኔ አባት ግን አንድ ጠረጴዛ ነገር አጠገብ ይቆማል፤ የሆነ ነገር በፓወር ፖይንትያሳያል፤ አንድ ጊዜ ይጨበጨብለታል፡፡ በቃ፡፡ አንድም የሚጨፍር ሰው አይታይም፡፡ አባዬ ግን ምንድን ነው?

ቆይ ግን እኛ ቤት ኢቲቪዎች የማይመጡትለምንድን ነው? አባቴ አርቲስት ስላልሆነ ነው አይደል፡፡ የኔ አባትኮ እንኳን ለፋሲካ ለአርሂቡ ቀርቦ አያውቅም፡፡ እውነታቸው ነው፡፡በአርሂቡኮ አርቲስቶች ሲቀርቡ ‹እንትናዬ አድናቂህ ነኝ፣ እወድሃለሁ፤ ቀጣዩ አልበምህ መቼ ነው የሚወጣው? ምን ፊልም ልትሠራልንነው?›› የሚል ሰው ይደውልላቸዋል፡፡ አሁን አባዬ አርሂቡ ላይ ቢቀርብ ምን ሊባል ነው? ምን ተብሎ ሊጠየቅ ነው? ደግሞ ማንምአድናቂ አያገኝም፡፡ አልበም የለው፤ ፊልም የለው፣ ሰዎች በምን ያውቁታል፡፡

አባዬ ግን አርቲስት መሆን ነበረበት፡፡ዶክተርነት ምን ያደርግለታል፡፡ አርቲስት ቢሆን ኖሮ በኋላ ሲያረጅ ‹የክብር ዶክትሬት› ተብሎ ይሰጠው ነበር፡፡ ‹የክብር አርቲስት›ብሎ ግን ማንም አሁን አይሰጠውም፡፡ ዶክተርነት ይደረስበታል፡፡ አርቲስትነት ግን አይደረስበትም፡፡ እንዲያውም እነርሱ ሲጠሩ ‹ክቡርዶክተር› ነው የሚባሉት የኔ አባት ግን ‹ዶክተር› ብቻ ነው፡፡

እርሷ ይህንን ስታወጣና ስታወርድየቴሌቭዥኑ ፕሮግራም ጀመረ፡፡ ጋዜጠኛውም ‹እያዝናናን እናስተምራለን› ብሎ የጓደኛዋን ቤት አሳየ፡፡ ምንም እንኳን የተቀረጸው በጾምጊዜ ቢሆን ዶሮው፣ በጉ፣ ክትፎው፣ ቅቤው፣ ዕንቁላሉ ይታያል፡፡ ለነገሩ እንደ ኢቲቪ አቆጣጠር ጾሙ አንድ ሳምንት ሲቀረው ያልቃል፡፡ከዚያ በኋላ ቀረጻ ይቻላል፡፡ ጓደኛዋን አየቻት፡፡ ቤታቸው እየታየ ነው፡፡
እየሮጠች አባቷን ቀሰቀሰቺው፡፡
‹‹ጓደኛዬ በቴሌቭዥን እየታየችነው›› ስትለው ድካሙ ባይለቀውም እርሷን ለማስደሰት ተነሥቶ ዓይኑን እያሸ ወደ ሳሎን መጣ፡፡ ‹እያት ኤልዳናን› አለቺው፡፡ ኤልዳናእየተጠየቀቺ ነው፡፡ ቃለ መጠይቁ ሲያልቅ ‹አባዬ አንተ መቼ ነው በቲቪ የምትቀርበው› አለቺው ልጁ፡፡

‹‹ሚዲያችን ከታዋቂ ይልቅ ለዐዋቂቦታ ሲኖረው›› አላት አባቷ፡፡
‹‹አንተ ግን ለምን ታዋቂ አልሆንክም››

‹‹ልጄ እኔኮ ታዋቂ ነኝ፡፡ የኢቲቪጋዜጠኞች ግን አያውቁኝም፡፡ የቢቢሲ፣ የሲኤንኤን፣ የአልጀዚራ ጋዜጠኞች ያውቁኛል፡፡ እኔ አንድ ነገር ስለ ግብርና ከተናገርኩ ወይምከጻፍኩ ያ ዜና ይሆናል፡፡ እዚህ አገር ግን ዕውቀት ዜና አይሆንም ልጄ፡፡ እዚህ ሀገር ዜና የሚሆነው ፖለቲካና ቀልድ ነው፡፡››
‹‹እሺ ለምን አርሂቡ ላይ አትቀርብም››
‹‹ያማ ጋዜጠኛውን ማሰቃየት ነውልጄ››
‹‹ለምን ይሰቃያል?››

‹‹ምን ይጠይቀኛል? ጥናታዊ ጽሑፎቼንማንበብ ሊኖርበት ነው፡፡ ምርምሮቼን መቃኘት ሊኖርበት ነው፡፡ ስለ እኔ የተሰጡ የሌሎች ሳይንቲስቶችን ምስክርነት ማገላበጥ ሊኖርበትነው፡፡ ይሰቃያል ልጄ፡፡ ቀልድ የለመደን ሰው ዕውቀት ያሰቃየዋል፡፡በቀለላሉ የመጀመሪያ አልበምህ መቼ አወጣኸው? የመጀመሪያው ፊልምህምን ነበር? ገጠመኝህ ምንድን ነው? እያለ ሰዓቱን መሙላት ሲችል ምን በወጣው ሳይንቲስ አቅርቦ ይሰቃያል፡፡ ጋዜጠኞቹ መዘጋጀትስለማይችሉም ስለማይፈልጉም አይደል እንዴ ‹እስኪ ራስሽን ለአድማጮች አስተዋውቂ› የሚሉሽ፡፡ ይኼኮ የጋዜጠኛው ሥራ ነበር፡፡ አንብቦ፣ ፕሮፋይል ሠርቶ ቢመጣ ኖሮእንዲህ አይልም፡፡ ደግሞም አለቆቹም ላይወዱለት ይችላሉ፡፡ ዕውቀት የመለወጥ ኃይል አለው፡፡ ሕዝቡ ደግሞ እንዲዝናና እንጂ እንዲለወጥ አይፈለግም፡፡››
‹‹ተዪው እኔን፡፡ አንድ ገበሬበዓል እንዴት ነው የሚያከብረው? ድንበር ላይ ባሉ ወታደሮች ዘንድ እንዴት ይከበራል? ተረኛ ሆነው ሆስፒታል ወይም እሳት አደጋመከላከያ ውስጥ ባሉ ባለሞያዎች ዘንድ ፋሲካ ምን ዓይነት በዓል ነው? በዕለቱ አየር ላይ በሚሆኑ የአውሮፕላን አብራሪዎችና አስተናጋጆች፣መርከብ ላይ በሚሠሩ ኢትዮጵያውያን፣ ሆስፒታል በተኙ ሕሙማን፣ በዓል እንዴት ይከበራል? የሚለውን እንኳን መች ያሳዩናል፡፡ ለምንይመስልሻል?

‹‹እነርሱ ታድያ አርቲስት ናቸውእንዴ?››

ልጄ የኑሮ አርቱማ ያለው እዚያውስጥ ነበር፡፡ የኛነታችንን ሌላ ገጽታ የምናየውማ እዚያ ውስጥ ነበር፡፡ ግን ይኼ ማሰብ ይጠይቃል፤ መመራመርን፣ ማንበብን፣ መዘጋጀትንይጠይቃል፡፡ ማሰብ፣ ማንበብና መዘጋጀት ደግሞ እዚያ ቤት የሚወደዱ አይመስሉኝም››
‹‹እሺ ታድያ መቼ ነው የኛ ቤትበቴሌቭዥን የሚቀርበው?››
‹‹ወይ እኔ መቀለድ፣ ወይ እነርሱማወቅ ሲጀምሩ››

The post የሳይንቲስቱ ልጅ ጥያቄ – ከዳንኤል ክብረት (ዲ/ን) appeared first on Zehabesha Amharic.

በደቡብ አፍሪካም እንዲህ ሆነ – (ሄኖክ የሺጥላ)

$
0
0

ethiopia south africa
ከ 17ኛው ክፍለ ዘመን እስከ በቀደም በነጮች ( በመጀመሪያ በ-ቡሮች ወይም ደቾች ቀጥሎም በ 19ኛው ክፍለ ዘመን የአልማዝ መገኘትን ተከትሎ በእንግሊዞች ) የባርነት ቀንበር ስር ስትማቅቅ የኖረችው ደቡብ አፍሪካ ፣ በብረት እሾህ ታጥራ ልጆቿን በስልጡን የጀርመን ውሻዎች (Geremen Shippered) ስታዘነጥል የኖረችው ደቡብ አፍሪካ ፣ ነጭ ባለፈበት እንዳታልፍ ፣ እንዳትማር ፣ እርስ በእርስ እንዳትነጋገር ፣ ህዝቦቿ በገዛ ሀገራቸው አራተኛ ወይም የመጨረሻ ዜጋ ተደረገው ( ከ እንግሊዝ ፣ ከደች ፣ ከ ሕንድና ኤስያ ቀጥሎ ) ለመቶ አመታቶች ነጻነት ምን እንደሆነ ሳታውቅ የኖረችው ደቡብ አፍሪካ ፣ ነጻነትን ከትናንት ወዲያ ያገኘች ው ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦጠሊቃዊ ፣ ሰላማዊ ፣ ሰዋዊ ስብሰባዎችም ሆነ ማንኛውም የሰለጠነ እና እንደሰው የሚኖር ሰው የሚያደርጋቸው ተፈጥሯውዊ ክንውኖች ተነፍጏት የኖረችው ደቡብ አፍሪካ ( ለምሳሌ እኔ ደቡብ አፍሪካ በነበርኩበት ግዜ ሴቶቹ ደቡብ አፍሪካውያን ሲሰክሩ በአብዛኛው በቁማቸው እንደሚሸኑ አይቻለሁ )፣ አዎ ያቺ የባርነት ተምሳሌት ፣ የመረገጥ እና የውርደት ቤት የነበረችው ደቡብ አፍሪካ ፣ ከመሬቷ ሲሶ ያህሉ እንኩዋ የሷ ያልሆነው (ያልነበረው ) ፣ የምድሯን በረከት ፣ የልጆቿን ደም ፣ አንጡራ ሀብት በሉት ፣ እምቅ ሀብት ፣ ወርቁን እና ፣ አልማዙን ቆፍረው እና አጥለው ፣ ኖራውን እና የድንጋይ ከሰሉን በድማሚት አፍርሰው ፣ ረስተንበርግን እንደ ኩይሳ ከላይ ያፈር ክምር ፣ ከስር የምስጥ ቤት አስመስለው ፣ ጆሃንስበርግን ( ወይም ኢጎሊን ) የወርቅ ምድር እያሉ እያሞካሹ ህዝቦቿን እያሹ ኑረው ፣ ኑረው የተትረፈረፉባትን ጌታዎቿን ፣ ደምና ውስኪ እኩል ያፈሰሱባትን ገዳዮቿን ይቅርታ ያለችው ያቺ ሳውዝ አፍሪካ ፣ የዘመን በደሏን ረስታ ፣ የባርነት ቀንበር ህሊናዋ ላይ ክርክር ቢሰራም ፣ በፍቅር ተረታሁ ፣ ሰውነት ከበደል እና ከክፉ ታሪክ በለጠብኝ ብላ ፣ በ ጁሃን ስበርግ ( በሱዌቶግዛት ወይም ከተማ )፣ በ-ደርባን ፣ በ ፖርት ዔልዛቤት ፣ በ ኬፕታወን ፣ በዋና ከተማው በፕሪቶሪያ ፣ በራንጉሌ ፣ በጃካራንዳ፣ በሮቢን ደሴት ፣ እና በወዘተ፣ እነ ሜምቄጺ፣ እኔ ሲቦንጊሌ ፣ እነ ታቱ ፣ እነ ዙማ ፣ እነ ማዲባ ፣ እነ ወዘተ በባቡር መሳፈርያው ሆነ ፣ በአሳንሱር ላይ ፣ በመንገድ ላይ ሲጏዙም ሆነ አምጠው ሲወልዱ ፣ በዚህ በኩል እንዳትሄዱ ፣ በዚህ በኩል ሂዱ ( NET NIE BLANKES ( None white person only blacks ) ) እየተባሉ የኖሩት ደቡብ አፍሪካውያን ፣ በአንድ ምህረት ፣ ሁለት ገጽ የይቅርታ ደብዳቤ ተቻችለው መኖር የለመዱት ደቡብ አፍሪካውያን ፣ ሲቸገሩ ድንበር አቋርጠው ያስጠጏቸውን ሞዛምቢኮች ፣ መሳሪያ ደብቀው ያሸገሩላቸውን ዚምቡዋቤዎች ፣ መሪዎቻቸውን ወስደው ያሰለጠኑላቸውን ኢትዮጵያውያኖች ዛሬ በእሳት አቃጠሉ ፣ በድንጋይ እንደ ዘማይ በአደባባይ ወገሩ ፣ እንደ ጌቶቻቸው እነሱም የባርነት ግፋቸውን ፣ ያደፈ ልባቸውን ፣ ያቄመ ልቦናቸውን በወንድሞቻቸው ላይ አነሱ ።

እንደ እንሰሳ ለዘመናት የገዟቸውን ፣ እንደ ትል የረገጧቸውን ፣ እንደ ትቢያ ያረከሷቸውን ፣ አጥንታቸውን የከሰከሱትን ፣ ደማቸውን የመጠጡትን ፣ እምቅ ሀብታቸውን የዘረፉትን ይቅርታ ማድረግ ያልከበዳቸው ደቡብ አፍሪቃውያን ፣ ዛሬ ግን በደም እና በቀለም የሚመስሏቸውን ፣ በችግር የደረሱላቸውን ፣ በ ጨለማ መብራት የሆኑላቸውን ፣ አብረዋቸው የመከራ ጽዋ ( ገፈት ) የቀመሱ አፍሪካዊ ወንድሞቻቸውን አይን ማየት አስጠላቸው ፣ ህጻናትን የፈጁትን የአፓርታይድ መሪዎች ፣ ወታደሮች ፣ እና ወዘተ ይቅርታ ማድረግ ያልከበዳቸው ደቡብ አፍሪቃውያን ፣ በቢሊዮን ምናልባትም በትርሊዮን ዶላሮች የሚቆጠር ገንዘብ ለመቶ አመታት የዘረፏቸውን ፣ የወረፏቸውን እንደ እንስሳ ያዩዋቸውን ቀኝ ገዢዎች ይቅርታ ማለት ግድ ያላላቸው ደቡብ አፍሪቃውያን ፣ ዛሬ ጨርቅ ነግዶ ፣ በየ ቅያሱ ( ሎኬሽን ) ብርድ-ልብስ አዙሮ ፣ ነጠላ ጫማ በየ መንገዱ አንጥፎ ፣ ቻፓቲ ሸጦ ህይወቱን ለማሸነፍ የሚውተረተረው ጥቁር ንብረት አስቆጣቸው ፣ በሱዌቶ የህጻን ልጅ ደም በ መትረየስ ( አውቶማቲክ ጠብ መንጃ ) የቀጠፈውን አፓርታይድ ይቅርታ ማድረግ ያልከበዳቸው ደቡብ አፍሪካውያን ፣ we are passionate about South Africa የሚል ጽሑፍ ሽንጡ ላይ ለጥፎ በጎዳናዋ ላይ የሚሽከረከረው የመአድን መጫና ባቡር ሳይሆን በብሪ ፣ ዴሊቨር እና ጂፒ ጎዳናዎች ላይ የተከፈቱት ጥቃቅን ሱቆች ደማቸውን አፈላው።

የሚከተሉትን ሕጎች የተቀበሉት (Population Registration Act, 1950 – This Act demanded that people be registered according to their racial group. This meant that the Department of Home Affairs would have a record of people according to whether they were White, Coloured, Black, Indian or Asian. People would then be treated differently according to their population group, and so this law formed the basis of apartheid. It was however not always that easy to decide what racial group a person was part of, and this caused some problems.

Group Areas Act, 1950 – This was the Act that started physical separation between races, especially in urban areas. The Act also called for the removal of some groups of people into areas set aside for their racial group. Well known removals were those in District Six, Sophiatown and Lady Selborne (also see Cato Manor, Fietas and Curries Fountain (Grey Street area)). People from these areas were then placed in townships outside of the town. They could not own property here, only rent it, as land could only be white owned.

Promotion of Bantu Self-Government Act, 1959 – This Act forced different racial groups to live in different areas. Only a small percentage of South Africa was left for black people (who comprised the vast majority) to form their ‘homelands’. Like the Group Areas Act, this act also got rid of ‘black spots’ inside white areas, by moving all black people out of the city. This Act caused much hardship and resentment. People lost their homes, were moved off land they had owned for many years and were moved to undeveloped areas far away from their place of work.

Bantu Education Act, 1953 – established an inferior education system for Africans based upon a curriculum intended to produce manual laborers and obedient subjects. Similar discriminatory education laws were also imposed on Coloureds, who had lost the right to vote in 1956, and Indians. The government denied funding to mission schools that rejected Bantu Education, leading to the closure of many of the best schools for Africans. In the higher education sector, the Extension of University Education Act of 1959 prevented black students from attending “white” universities (except with government permission) and created separate and unequal institutions for Africans, Coloureds, and Indians respectively. The apartheid government also undermined intellectual and cultural life through intense censorship of books, movies, and radio and television programs.

The Suppression of Communism Act, 1950 (originally introduced as the Unlawful Organisations Bill) – The Act was introduced in an attempt to curb the influence of the CPSA and other formations that opposed the government’s apartheid policy. It sanctioned the banning/punishment of the CPSA or any group or individual intending to bring about political, economic, industrial and social change through the promotion of disorder or disturbance, using unlawful acts or encouraging feelings of hostility between the European and non-European races of the Union of South Africa. The Act was progressively tightened up in 1951, 1954, and yearly from 1962-1968.
) እና ለነዚህም ይቅርታ ያደረጉት ደቡብ አፍሪቃውያን ፣ የጥቁር ወንድሞቻቸው ገላ ላይ እሳት ጫሩ ።

መደምደሚያ

ጥንትስ ቢሆን ሰው ወገኑን ካዋረደ ለግፍ ጥሎ
ባለቤት ያቀለለውን ባለ ዕዳ መች ተቀብሎ ! ይላል አባት ዓለም ጸጋዬ ገ/መድህን ። እኛም

ባገራችን በአድ ሆነን በመአዳችን ቀላዋጭ
በሰው ሀገር የሰው ዝቃጭ !

ሀገር የሌለው ክብር ፣ ዘር ፣ ሕይወት እና ተስፋ የለውም ! የትም የኛ አይደለም ! የኛ ኢትዮጵያ ብቻ ነች !
ለነጻነታችን ካልተጋን ፣ ካልተዋጋን ፣ በየመን የሰማይ እሳት ፣ በቀይባይ ባህር የመአበል እሳት ፣ በሳውዲ አረቢያ የሹርጣ እሳት ፣ በ ሳውዝ አፍሪካ የቆራጣ ባርያ እሳት ይበላናል ። ሀገር ይኑረን ! ነጻነታችንን እናስመልስ !

ሄኖክ የሺጥላ

The post በደቡብ አፍሪካም እንዲህ ሆነ – (ሄኖክ የሺጥላ) appeared first on Zehabesha Amharic.

እንኳን ደቡብ አፍሪካ አልሆንሽ ! [ካልሆነሽ] – (ቴዲ ድንቅ) –አትላንታ

$
0
0

ከጥቂት ወራት በፊት አንዲት እህታችን “መጀመሪያ እንትን ነኝ” እንጂ ኢትዮጵያዊ አይደለሁም ስትል ባንዲራ ስታቃጥል፣ ተንቀሳቃሽ ምስሏን ፌስ ቡክ ላይ መለጠፏ ይታወሳል። ይህች እህታችን እንኳን በዚህ ሰአት ደቡብ አፍሪካ አልሆነች። [ካልሆነች]
south africa

south africa news

South Africa Immigrants Attacks
ደቡብ አፍሪካውያን ካገራችን ውጡ እያሉ በጎራዴና በገጀራ ሲቆራርጡና ፣ በ እሳት ሲያጋዩ የታዩት ፣ ኢትዮጵያዊ የሆነውን ሁሉ ነው። “መጀመሪያ እንትን ነኝ” ብሎ የጎሳ ስም ጠርቶ ያመለጠ ሰው የለም። እነሱም የሚያውቁን (ደግሞም የሆነነውን) ኢትዮጵያዊነታችንን እንጂ ጎሳችንን አይደለም። ያቺ ባንዲራ ያቃጠለች ውብ ኢትዮጵያዊት፣ የጎሳዋን ስም ጠርታ ልታመልጥ አትችልም፣ ደቡብ አፍሪካውያንም ሆነ ሌላው ዓለም የሚያውቃት፣ እሷ ብትክደውም፣ በኢትዮጵያዊነቷ ነው።

በጎሳው ምክንያት ከደቡብ አፍሪካው እልቂት የተረፈ የለም። “መጀመሪያ አማራ ነኝ፣ መጀመሪያ ጉራጌ ነኝ፣ መጀመሪያ ትግሬ ነኝ፣ መጀመሪያ ኦሮሞ ነኝ .. ወላይታ ነኝ .. ሃረሪ ነኝ ..” በፈተና ሰአት አያድንም። ዓለም የሚያውቀን፣ ደቡብ አፍሪካዎቹም ውጡልን ብለው ያረዱን በኢትዮጵያዊነታችን ነው።

ያቺም እህታችን በዚህ ክፉ ሰአት ደቡብ አፍሪካ ብትሆን ኖሮ የአንዱ ገጀራ ሰለባ ልትሆን ትችል ነበር። ምክንያቱም ኢትዮጵያዊት ነቻ! ከሳውዲም በጅምላ እየተገረፍን ስንባረር “ኢትዮጵያዊ አይደለሁም፣ ከዚህ ጎሳ ነኝ” ብሎ የተረፈ ሰው አልነበረም። እናም እህቴ በዚህ ወቅት ደቡብ አፍሪካ ካልሆንሽ – በኢትዮጵያዊነትሽ መጤ ተብለሽ ይህን ሰአት የችግሩ ሰለባ ትሆኚ ነበረና በመትረፍሽ ደስ ብሎኛል – ያገሬ ልጅ ነሻ!

ግን ምናልባት … ምናልባት .. ድንገት ደቡብ አፍሪካ ያለሽ ከሆነና ንብረትሽ ተዘርፎ አንቺም ውጪ ተብለሽ ችግር ውስጥ ከሆነ ያለሽው .. እየጮህን ያለነው፣ ሰልፍ የምንወጣው፣ አይዟችሁ እያለን የምንጸልየው፣ የምናለቅሰውና ይህ ሁሉ ወገንሽ እያዘነ ያለው ፣ ላንቺም ጭምር መሆኑን ተረጂልን።

The post እንኳን ደቡብ አፍሪካ አልሆንሽ ! [ካልሆነሽ] – (ቴዲ ድንቅ) – አትላንታ appeared first on Zehabesha Amharic.

“አምባሳደሩ ወዳገራቸው መመለስ አለባቸው” የናይጄሪያ እንደራሴዎች “አሁን የተፈጠረው ጊዜያዊ ክስተት ነው” ሃይለማርያም

$
0
0

* “ወደ አገራቸው መመለስ ለሚፈልጉት ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን” ቴድሮስ አድሃኖም

በደቡብ አፍሪካ በሚገኙ አፍሪካውያን ላይ የተጀመረው ጥቃት ያስቆጣቸው የናይጄሪያ እንደራሴዎች በደቡብ አፍሪካ የሚገኙት አምባሳደር ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ውሳኔ አስተላለፉ፡፡ የሩዋንዳውን ፕሬዚዳንት በማስተናገድ የተጠመዱት ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ደሳለኝ በደቡብ አፍሪካ “የተፈጠረው ጊዜያዊ ችግር ነው ብለን እናምናለን” በማለት አስተያየት ሰጡ፡፡ ውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴድሮስ ከየቦታው ሃሳብ እየሰበሰብኩ ነው፤ “ወደ አገራቸው መመለስ ለሚፈልጉ ድጋፍ እናደርጋለን” አሉ፡፡ በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ግን የመመለስ ፍላጎት እንደሌላቸው ይናገራሉ፡፡
south africa news
ሰሞኑን በደቡብ አፍሪካ የተነሳው አሰቃቂ ግድያና ዘረፋ ብዙዎችን እኤአ በ2008 የተከሰተውን እንዲያስታውሱ አድርጓቸዋል፡፡ በወቅቱ ከስድሳ በላይ አፍሪካውያን የተገደሉና የበርካታዎች ንብረት የተዘረፈ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ሰሞኑን በተነሳው ሁከት ሶስት ኢትዮጵያውያን መሞታቸውንና አስከሬናቸውን ወደ ኢትዮጵያ መላኩን ከዚያው የወጡ መረጃዎች ቢጠቁሙም የኢህአዴግ ባለሥልጣናት ግን የሞተው አንድ ብቻ ነው ማለታቸውን ኢቲቪ ዘግቧል፡፡

ከኢትዮጵያውያኑ ሌላ ዜጎቿ እንደሞቱባት የምትጠቀሰው ናይጄሪያ በድርጊቱ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጅቶች እያደረገች መሆኑ ተሰምቷል፡፡ የናይጄሪያ እንደራሴዎች በደቡብ አፍሪካ ላይ የከረረ እርምጃ እንዲወሰድ እየሞገቱ ነው፡፡ የናይጄሪያ ተወካዮች ምክርቤት በጉዳዩ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ካደረገ በኋላ በደቡብ አፍሪካ የሚገኙት የናይጄሪያ አምባሳደር ወደ አገራቸው እንዲመጡ አጽድቋል፡፡

sa2sa4በተለያዩ ድረገጾች ላይ የተነበበው ይህ ዜና እንደሚያስረዳው የተከበሩት እንደራሴዎች እጅግ በጋለና አገር ፍቅር ስሜት በወገኖቻቸው እንዲሁም በአፍሪካውያን ላይ የሚደርሰውን ጥቃት አውግዘዋል፤ ኮንነዋል፡፡ የኤዶ ግዛት እንደራሴ ረቂቅ ሕጉ ላይ የናይጄሪያ መንግሥት ከደቡብ አፍሪካ ጋር ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲያቋርጥ የማሻሻያ ሃሳብ አቅርበው ነበር፡፡ ሃሳቡን የዴልታው እንደራሴ በአጽንዖት የደገፉ ቢሆንም ውሳኔ ድምጽ ላይ ሲደርስ አምባሳደሩ ወደ አገራቸው በአስቸኳይ እንዲጠሩ የሚለው ሲያልፍ ማሻሻያው ግን በቂ ድምጽ ሳያገኝ ቀርቷል፡፡ ማሻሻያውን የደገፉ እንደራሴዎች በጉዳዩ ላይ እንደሚሰሩ የተሰማ ቢሆንም አምባሳደሩን ወዳገራቸው ማስመጣቱ በፍጥነት እንዲፈጸም ፕሬዚዳንት ጉድላክ ዮናታን የጉዳዩን አስቸኳይነት ለፕሬዚዳንት ያዕቆብ ዙማ እንዲገልጹ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

በኢትዮጵያ ጉብኝት የሚያደርጉትን የሩዋንዳ ፕሬዚዳንት እያስተናገዱ ያሉት ሃይለማርያም ደሳለኝ በደቡብ አፍሪካ የደረሰውን በተመለከተ በእንግሊዝኛ ድምጻቸውን አሰምተዋል፡፡ ጠ/ሚ/ሩ ታሪክን የዘነጋ በሚመስል ለስላሳ አነጋገር “ደቡብ አፍሪካ ከቅኝ አገዛዝም ሆነ ከአፓርታይድ አገዛዝ ነጻ እንድትወጣ ድጋፍ መስጠታችን ይሰማናል” በማለት አጭሩን ንግግራቸውን አሰምተዋል፡፡ ሲቀጥሉም “አፍሪካውያን በፈለጉበት መኖር” እንደሚችሉ ከገለጹ በኋላ “አሁን የተፈጠረው ጊዜያዊ ክስተት ነው ብለን እናምናለን፤ የደቡብ አፍሪካ መንግሥትና ፓርቲ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ እንጠብቃለን” በማለት ወደ ግብዣቸው ተመልሰዋል፡፡

በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት አራተኛዋ ባለሥልጣን የሆኑትን የበታች ጸሃፊ ዌንዲ ሸርማንን በማስተናገድ የተጠመዱት ቴድሮስ አድሃኖም በፌስቡክ በለቀቁት አጭር መልዕክት “በደቡብ አፍሪቃ ከሚገኙ አንዳንድ ወገኖች” ጋር በስልክ እየተነጋገሩ መሆናቸውን እና ምን መደረግ እንዳለበት ከየቦታው እስካሁን ሃሳብ በመሰብሰብ ሥራ ላይ መጠመዳቸውንsouth-africa-foreigners የሚገልጽ እንደምታ ያለው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ “ወደ አገራቸው መመለስ የሚፈልጉትን” ለመደገፍ መዘጋጀታቸውን በዚሁ መልዕክት ገልጸዋል፡፡
ነዋሪዎችን ከየመኖሪያቸው በማፈናቀል፤ መኖሪያ በማሳጣት እና በግዳጅ ባልፈለጉበት ቦታ በማስፈር የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸሙ በተለያዩ ዘገባዎች በማስረጃ የሚነገርለት ኢህአዴግ ወደ አገር ለመመለስ ለሚፈልጉ ዝግጅቱ ማድረጉን ቢገልጽም በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ግን ሁኔታው አስፈሪ ቢሆንም ወደ አገራቸው መመለስ እንደማይፈልጉ ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ አንዳንዶችም “ከአገራችን የወጣነው የኢኮኖሚ ጥገኝነት አስገድዶን ብቻ አይደለም፤ የመኖር ኅልውናችን አደጋ ላይ በመውደቁም ጭምር ነው” ሲሉ ተሰምተዋል፡፡
ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንዳሉት “ደቡብ አፍሪካውያን ኢትዮጵያዊ ስለተባልን አገር ያለን መስሏቸው ከአገራቸው እንድንወጣ ይነግሩናል፤ በህይወት እያለን ወደ ኢትዮጵያ ሄደን በደኅንነት መኖር ስለማንችል እኮ ነው ስንሞት አስከሬን የምንልከው፤ ይህንን ግን የተረዱት አይመስለኝም” በማለት ሃሳባቸውን ተናግረዋል፡፡

sa9እኤአ በ2000 መጀመሪያዎች አካባቢ በአገራቸው የሚኖሩ ነጭ ሰፋሪዎችን ያባረሩት የዚምባብዌው ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ በዚሁ የደቡብ አፍሪካ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ዜጎቿ ደቡብ አፍሪካ እንደሚኖሩ የሚነገርላት ዚምባብዌ የዜጎቿን ጉዳይ ቀዳሚው ስፍራ የሰጠችው መሆኑ ተሰምቷል፡፡ በተለይ ግን ሙጋቤ ጉዳዩን አስመልክቶ በላኩት መልዕክት እንዲህ በማለት በደቡብ አፍሪካውያን ላይ ተሳልቀዋል፤ ዘልፈዋቸውማል፡፡

“ደቡብ አፍሪካውያን አንድ ነጭ በህይወት እያለ በጥፊ ለመምታት ሙከራ እንኳን ስለማያደርጉ (ስለሚፈሩ) ነጭ ሲሞት ሃውልቱን ይደበድባሉ፤ ነገር ግን አንድ ጥቁር የሌላ አገር ዜጋ በመሆኑ ብቻ በድንጋይ ወግረው ይገድላሉ፡፡”

Source: googlgule.com

The post “አምባሳደሩ ወዳገራቸው መመለስ አለባቸው” የናይጄሪያ እንደራሴዎች “አሁን የተፈጠረው ጊዜያዊ ክስተት ነው” ሃይለማርያም appeared first on Zehabesha Amharic.

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በሚኒሶታ እያደረጉት ያለውን ሕዝባዊ ስብሰባ በቀጥታ ይከታተሉ (Live)

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live