Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የዞን 9 ጦማሪያኑና ጋዜጠኞቹ የክስ መቃወሚያ ቀጠሮ ተላለፈ

$
0
0

የዞን ዘጠኝ ስድስት ጦማርያንና ሶሰት ጋዜጠኞች በወንጀለኛ መቅጫ ህግና በፀረ ሽብር አዋጁ ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ የሽብር ወንጀል ለመፈፀም አቅደዋል፣ ተዘጋጅተዋል፣ አሲረዋል፣ አነሳስተዋል እንዲሁም ህገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በሁከትና በአመፅ ለመለወጥ አስበዋል ተብለው በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት በህገ መንግሥትና በህገ መንግሥታዊ ሥርዓት ላይ በሚደረግ የሙከራ ወንጀል ተከሰው ባለፈው ሐምሌ 11 ቀን 2006 ዓ.ም ፍርድ ቤት መቅረባቸው ይታወሳል፡፡
zone9-e1398747809895
ከሦስት ወራት የምርመራ ጊዜ በኃላ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 8ኛ የወንጀል ችሎት የቀረቡት ተከሳሾች በፅሑፍ የቀረበላቸውን ክስ ካደመጡ በኃላ በአቃቢ ህግና በጠበቆቻቸው መካከል በተደረገ የዋስትና ጥያቄ ክርክር ብይን ለመስጠትና የክስ መቃወሚያ ለማዳመጥ ፍርድ ቤቱ ለሐምሌ 28 ቀን 2006 ዓ.ም የጊዜ ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል፡፡

በዛሬው ቀጠሮ ዘጠኙም ተከሳሾች ፍርድ ቤት የቀረቡ ቢሆንም በዋስትና መብት ጉዳይ በጠበቃና በአቃቢ ሕግ መካከል የተደረገው ክርክር የህግ ትርጓሜ እንደሚያስፈልገው ጠበቃዎች በጠየቁት መሰረት ከመቅረጸ ድምጹ ላይ ተገልብጦ ለህግ አስተርጓሚ እንዲላክ እንዲሁም በሌለችበት ክስ የተመሰረተባት 1ኛ ተከሳሽ ሶሊያና ሽመልስ በጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላት የተሰጠው ትዕዛዝ ባለመፈፀሙ ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ባለፈው ቀጠሮ ተከሳሾች የክስ መቃወሚያቸውን እንዲያቀርቡ ከፍርድ ቤቱ ብይን ተሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ በዛሬው ቀጠሮ የሰጣቸው ትዕዛዞች ተፈጻሚ ባለመሆናቸው ለብይን ያስቸግረናል በሚል የክስ መቃወሚያቸውን ሳያደምጥ ቀርቷል፡፡

ጠበቆቹ ለፍርድ ቤቱ በሰጡት አስተያየት በመጀመሪያው የፍርድ ቤት ውሎ ለዛሬ ቀጠሮ የክስ መቃወሚያ እንዲቀርብ ብይን የተሰጠ መሆኑን አስታውሰው ፍርድ ቤቱም ሆነ አቃቢ ህጉ የክስ መቃመወሚውን ለማየት በቂ ጊዜ የሚሰጥ በመሆኑ የክስ መቃወሚያ በጽሁፍ እንድናቀርብ ይፈቀድልን ብለው ጠይቀዋል፡፡ ችሎቱም የጠበቆችን ጥያቄ በመቀበሉ የክስ መቃወሚያው ለአቃቢ ህግና ለፍርድ ቤቱ በጽሁፍ ቀርቦ በቀጣዩ ቀጠሮ በንባብ እንዲሰማ አዟል።

በ1ኛ ክስ ላይ ለተዘረዘሩ የወንጀል ድርጊቶች 5 መቃወሚያ እንዲሁም በ2ኛ ክስ ለቀረቡት የወንጀል ድርጊቶች 4 መቃወሚያ ነጥቦች የተዘረዘረበት ሰነድ “የቀረበው ክስ ከተጠቀሰው የህግ አነጋገር ጋር የሚቀራረብ አለመሆኑን፣ ተከሳሾች ፈጽመዋቸዋል የተባሉት በክስ ዝርዝሩ የተመለከቱ ተግባራት በህግ የተፈቀዱና ሕገ መንግስታዊ ጥበቃም የተደረገባቸው ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች መሆናቸውን፣ የቀረበው ክስ ግልፅ አለመሆኑን፣ ወስደዋል የተባሉት ሥልጠናዎችና ለመገናኛ ብዙኃን ያስተላለፉት መረጃ ወንጀል አለመሆኑን የተመለከቱ መቃወሚያዎችን የያዘ ነው፡፡
በ2ኛ ክስ የቀረበው የክስ መቃወሚያ ደግሞ ጠበቃው ማሰብ የማያስከስስና የማያስቀጣ መሆኑን፣ መደራጀት፣ የሥራ ክፍፍል መፍጠር እና የተለያዩ ሥልጠናዎችን መውሰድ ወንጀል አለመሆኑን፣ በአንድ ድርጊት ሁለት ክስ መቅረቡ አግባብ አለመሆኑ፣ የቀረበው የማስረጃ ሰነድ አለመሟላትን በተመለከተ ከወንጀለኛ መቅጫ እና ከጸረሽብር አዋጁ አንቀጽ ጠቅሰው ተቃውሞዎቻቸውን በጽሑፍ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

የዕለቱን ችሎት የሚመሩት ዳኛ ባስተላለፉት ውሳኔ የዋስትና መብት ጥያቄ ክርክር ከመቅረጸ ድምጽ ተገልብጦ ከመዝገቡ ጋር ተያይዞ ለህግ አውጪ አካል እንዲልክ እንዲሁም ለ1ኛ ተከሳሽ በፕሬስ ጥሪ እንዲደረግና የክስ መቃወሚያ በንባብ እንዲደመጥ ትዕዛዝ አስተላልፈው ለነሐሴ 14 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥተዋል፡፡

↧

↧

አዲስ መረጃ በአቶ በረከት ዙሪያ፡ ምስጢር አወጡ የተባሉትን የጂዳ ቆንስላ ጽ/ቤት እያመሰ ነው

$
0
0

ሰበር ዜና አቶ በረከት ስሞኦን ዛሬ August 5, 2014 የሆስፒታል ቀጠሮቸውን ያጠናቅቃሉ !
« በአቶ በረከት ጉዳይ ካድሬዎች ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤትን ሲያምሱ ዋሉ »

Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ

bereket alamudi demeke
ሳውዲ አረቢያ በህክምና ላይ የሚገኙት አቶ በረከት ስሞኦን ከህመማቸው አገግመው ሼክ አላሙዲን ወደ አዘጋጁላቸው ሚስጥራዊ ሆቴል ካቀኑ ወዲህ እኚህ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ስላሉበት የጤነነት ሁኔታ በእርግጠኝነት መናገር ባይቻለም ከሁለት ቀን በፊት የሼክ አላሙዲን ወደ አሜሪካ ማቅናት ተከትሎ የአቶ በረከት ስሞኦን የ ጤንነት ሁኔታ በመላካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ መረጃዎች ያመላክታሉ ። አቶ በረከት ስሞኦን እስካሁን ሳውዲ አረቢያ ከሚገኙ ዲፕሎማቶች ጋር በስልክም ሆነ በአካል እንዳለተጋናኙ የሚገልጹ እነዚህ ምንጮች እኚህ የመንግስት ከፍተኛው ባለስልጣን ያረፉበት ሆቴል ምሲጥራዊነቱ በከፍተኛ ጥንቃቄ የተጠበቀ መሆኑን ይናገራሉ።

የአቶ በረከት የጤንነት ሁኔታ በማህበራዊ ገጾች መነጋገሪያ ከሆነ ወዲህ ጭቀት ውስጥ የገቡት ሼክ አልሙዲን የተለያዩ ሆቴሎችን እየቀያየሩ እኚህን የመንግስት ባለስልጣን ደብቀው ሲያስታምሙ እና አሰፈላጊውን ድጋፍ ሲያደርጉላቸው መክረማቸውን ለማውቀ ተችሏል። አቶ በረከት ከሆስፒታል ከወጡ ወዲህ የተለያዩ ሆቴሎች እንዳረፉ የሚገልጹ መረጃዎች ሼኩ ወደ አሜሪካ ከማቅናታቸው በፊት በግል ከተከራዩላቸው ምርጥ ሆቴሎች ምናልባተም የመጨረሻ የአቶ በረከት ሚስጥራዊ ማገገሚያ ይሆናል ተብሎ ከሚነገርለት ሆቴል ነገ ወደ «ቡግሻን» hospital በማቅናት የመጭረሻ የህክምና ቀጠሮአቸውን ካጠናቀቁ በሃላ በአጭር ቀን ውስጥ፡ ወደ ሃገር ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተያያዘ ዜና በህክምና ላይ የምትገኘው የ6 አመቷ የአቶ በረከት ልጅ ህጻን ህሊና በረከት በመልካም ጤነት ላይ መሆኗን የኢትዮጵያ ሃገሬ የሆስፒታል ምንጮች አረጋግጠዋል ።

ይህ በዚህ እንዳለ በጅዳ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ካድሬዎች የአቶ በረከትን ገበና አጋለጣችሁ በሚል ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ዛሬ የመጡ ኢትዮጵያውያን ሲያዋኩቡ መዋላቸው በጅዳ እና አካባቢው ኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተናኛ ቁጣን ማስነሳቱ ን ለማረጋገጥ ተችሎል ። ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት የተለያዩ ጉዳዮቹን ለማስፈፀም በጠራራ ጸሃይ ሲነፍሩ የነበሩ ኢትዮጵያዊያንን እንደ ዜጋ አዝነው በአግባቡ ከማስተናገድ ይልቅ አቶ በረከት መታመማቸውን መረጃ ያወጣችሁት እናንተ ናችሁ የተቃዋሚ ወሬ አቀባዩች እናተን ሰብስቦ ማቃጠል ነበር በሚል ዛቻ ፍጹም ኢትዮጵያዊ ነኝ ከሚል የድርጀት አባል በማይጠበቅ ቃላት በኢ.ህ.ዴ.ን ካድሬዎች እና የህወሃት ካድሬዎች ሲያዋክቡ ሲዋከቡ መዋላቸውን በደሉ የተፈፀመባቸው ወገኖች ገልፀውልናል። በተለይ እራሳቸውን ብቸኛ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ፈላጭ ቆራጭ አድርገው ያስቀመጡት የህወሃት የቀድሞ ታጋይ አቶ ገሬ እና መዝገብ ቤት ሃላፊ የሆነው የትግራይ ተወላጁ የቀድሞው የህወሃት ታጋይ አቶ ሽፋ ባለጉዳዮችን ሲያንገራግሩ ከነበሩ መሃከል ግንባር ቀደም እንደነበሩ ታውቋል።

የጅዳ ቆንስል ሃላፊ የነበሩትን ቆንስል ዘነበን በተጽዕኖ ያስነሱት እንዚህ የጅዳ ኢህአዴግ ካድሬዎች የጅዳን ቆንስላ ጽ/ቤት በመቆጣጠር ደካማ ዲፕሎማቶችን በመናቅ እንዳሻቸው በማድረግ ከማድረጋቸውም በላይ ለጉዳይ የመጣውን ኢትዮጵያዊ ማጉላላት እና ፓስፖርት እስከ መንጠቅ የደረሱ ወንጀለኞች መሆናቸው በአብዛኛው የጅዳ ማህበረሰብ ዘንድ ይነገራል። ከዚህ መሰሪ ተግባራቸው ያልታቀቡት እንዚህ ግለሰቦች የአቶ በረከትን ለህክምና መምጣትን መረጃ አወጣችሁ የሚሏቸውን ወገኖች ወደ ቆንስላው ግቢ ሲገቡ በመተናኮል ሁከት ቀሰቀሱ ብለው ለማሳሰር በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ከጽ/ቤት የወጡ መረጃዎቻችን ጠቁመዋል።

Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ

↧

በዓሉ ግርማን ለመግደል ሴራ ያስፈልግ ነበር ወይ?

$
0
0

( ከተስፋዬ ተሰማ)

በቅርቡ በኢትዮ ሚዲያ የታዋቂው ጋዜጠኛና ደራሲ በዓሉ ግርማ አሳዛኝ ህልፈት/አሟሟት በተመለከተ “በዓሉ ግርማን የበሉት ጅቦች አልጮህ አሉ” በሚል ርእስ አንድ ጽሑፍ ቀርቦ ነበር። ይሄ ጽሁፍ የቀረበው በማን፣ በየትኛው የስነፅሁፍ ወይም የጋዜጠኝነት መስፈርት ተመዝኖ እንደሆነ ባይታወቅም “ድንቅ ጽሁፍ” የሚል ክብር ተሰጥቶታል። ይህን ጽሁፍ የፃፈው አበራ ለማ ይባላል። ጋዜጠኛና ደራሲ በዓሉ ግርማ በተገደለበት ዘመን በአንድ መስሪያ ቤት ህዝብ ግንኙነት ውስጥ ይሰራ የነበረ ነው።

አበራ ያቀረበውን ጽሁፍ ሳነበው ታዋቂው የህግ ባለሙያ አቶ አለማየሁ ዘመድኩን (አሌክስ) እየደጋገመ የሚነግረኝ ቀልድ ለበስ ቁምነገር ትዝ አለኝ፤ አሌክስ ለፍትህ የቆመ እውነተኛ ሰው ብቻ ሳይሆን ትልልቅ ቁምነገሮችን ለዛ ባለው ቀልድ የመግለጽ ችሎታም ያለው ሰው ነው። አሌክስና እኔ ብዙ ጊዜ ሻይ እየጠጣን ስለሃገራችንና ስለዓለም ሁኔታ የምናወራቸው የጋራ ወዳጆች አሉን። ሁለቱም ጋዜጠኞች ናቸው። አንደኛው ብዙ ነገር የሚያውቅ፣ በምክንያት የሚያምን፣ሃሳቡን በጥሩ ሁኔታ የሚገልጽ ነው። ሌላው ደግሞ ስሜታዊና አሰልቺ ነው። አሌክስ የሁለቱን ሰዎች ልዩነት ለዛ ባለው ቀልድ ለመግለጽ እንዲህ ይለኛል፤ «ስማ ምናለበት ጋዜጠኝነት እንደወታደርነት አስር አለቃ፣ ጄኔራል..የሚባል የማዕረግ ስም ቢኖረው?.አሁን እነዚህ ሰዎች ሁለቱም ጋዜጠኛ ይባላሉ?» ይለኛል፤
bealu girma 1
ጋዜጠኛ አበራ የፃፈው ፅሁፍ 16 ገጽ ያለው፣ በአራት ዋና ዋና ክፍል ተከፍሎ የሚታይ ነው። ፅሁፉን በአጭሩ፣ በጨዋነትና በቅንነት ስንፈትሸው ሶስት መልክቶችን በአንድነት የያዘ ይመስላል። በስነፅሁፍ አንድ ፀሐፊ በፅሁፉ ሊነግረን ከሚፈልገው መልክት ውጭ ሌሎች ተጨማሪና ዋና መልክቶች ሲኖሩት ፅሁፉ(intentional fallacy) አለው ይባላል። የአበራ ለማ ጽሁፍ የመጀመሪያ መልእክቱ ታዋቂው ደራሲና ጋዜጠኛ በዓሉ ግርማ የተገደለው የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ ኰ/ል መንግስቱ ሃ/ማርያም፣ በወቅቱ የነበሩ ከፍተኛ የደርግ ባለስልጣናት፣ ማንነታቸውን ግልጽ ያላደረገልን በዓሉን የሚጠሉ ሰዎች፣ ጥቅም የሚፈለጉ የበዓሉ ጓደኞች፣ የስራ ባልደረቦችና (በጊዜው የማስታወቂያ ሚ/ር መስሪያ ቤት ባለስልጣኖች የነበሩ) ሰዎች በመተባበር በተለየ ሴራ ነው። እኔ ይህን ሴራ ደርሼበታለሁ ነው።

ሁለተኛው መልእክቱ ደግሞ የበዓሉ አሟሟት ግልጽ እንዲሆን የደርግ ባለስልጣናት (በሱ አጠራር ትልልቆቹ ጅቦችና ጓደኞቹ፤ የስራ ባልደረቦቹ አሁንም በሱ አጠራር ትንንሾቹ ጅቦች በዓሉ እንዴት እንደተገደለ፣ ለምን እንደተገደለ፣ ማን እንደገደለውና ማን እንዳስገደለው ለኢትዮጵያ ህዝብና ለበዓሉ ቤተሰቦች ምስጢሩን የመናገር ታሪካዊ ግዴታ አለባቸው፤ እኛም እየጠበቅናቸው ነው የሚል ትእዛዝ አዘል ጥያቄና የአንድ ወገን ክስ ነው። የመጨረሻው ምናልባትም የዚህ ጽሁፍ ዋናው መልክት ጋዜጠኛ አበራ በተለያዩ ምክንያቶች ከቀድሞ የማስታወቂያ ሚ/ር አለቆቹና ከተወሰኑት ደራሲያን ጋር ያለውን ግጭት በቂም ደረጃ ይዞ፣ አሊያም ባለው የፖለቲካ አቋም በኢህአዴግ ውስጥ ያለውን ታማኝነት ለማሳየት እነሙልጌታ ሉሌን መስዋእት አድርጐ በኢህዴግ ለመሰዋት የበዓሉን ስም አስታኰ ስማቸውን ለማጥፋት የፃፈው ጽሁፍ ይመስላል።

በእርግጥ በኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ኢትዮጵያውያን ያለምንም ምክንያትና ያለበቂ ምክንያት የፍትህን አደባባይ እየታሰሩ፣ እየተገረፉና እየተገደሉ እንዲሁም አገዳደላቸው ምስጢር እንደሆነ ቀሮቷል። እንዳለመታደል ሆኖ ይህ አሳዝኝ ድርጊት አሁንም በኛ ዘመን ቀጥሏል። በደረግ ዘመን የአምባገነኖቹና ነፍስገዳዩቹ ሰለባ ከሆኑት ንፁሃን ዜጎች ውስጥ አንዳንዶቹ ለሃገራቸው ብዙ የደከሙና ሽልማት የሚገባቸው ነበሩ።በህይወት ቢኖሩ ለሃገራቸው ብዙ የሚጠቅሙ ነበሩ። በጣም የምንወደውና የምናደንቀው ታዋቂው ጋዜጠኛና ደራሲ በዓሉ ግርማም ያለበቂ ምክንያት በግፍ ከተገደሉት የሀገራችን ታላላቅ ሰዎች አንዱ ነው። የደራሲ በዓሉ ግርማ ጉዳይ የቤተሰቦቹ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ጉዳይ ነው። በዓሉ ግርማን የሚያክል በኢትዮጵያ ጋዜጠኛነትና ስነጽሁፍ ታላቅ ቦታ የነበረው ሰው እንደዋዛ ወጥቶ መቅረቱ ወይም ያለበቂ ምክንያት መገደሉ የሁላችንም ሃዘንና የልብ ስብራት ነው። የዚህን ታላቅ ሰው የአገዳደል ምስጢር ማወቅና ለማወቅ ጥረት ማድረግ መቀጠል ያለበት በመሆኑ ሁሉም ወገን ሃላፊነት እንዳለበት እሙን ነው።

በዓሉ ግርማ ከሞተ ከ30 አመት በኋላ የተፃፈው የጋዜጠኛ አበራ ለማ ጽሁፍ አሳዛኙን የበዓሉ ግርማን አሟሟት ምስጢር የሚፈታ ሳይሆን ነገሩን የበለጠ የሚያወሳስበውና አንባቢውን ግራ የሚያጋባ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።በአሉ ግርማ የተገደለው በሴራ ነው ብሎ ቃላቶችን እየቆራረጠና እየቀጠለ ሊያሳየን የሚፈልገው ነገር ምክንያታዊ ያለሆነና እውነትነት የሌለው ሁላችንም ከምናውቀው ወፍ በረር አሉባልታና ወሬ ያለፈ አዲስ ነገር የለውም። አፍ ሲከፈት ጭንቅላት ይታያል እንደሚባለው አንድ ሰው ሲናገር/ሲጽፍ የተናጋሪው ወይም የፃሀፊውን ማንነት ከፅሁፉ በቀላሉ መረዳት ይቻላል። አበራ ለማ ይህን ጽሁፍ ሲፅፍ የበዓሉ ግርማ አሳዛኝ የአሟሟት ምስጢር አሳዝኖትና አሳስቦት መሆኑን እንድንጠራጠር የሚያደርጉ ጭብጦች ግን አሉ።

በዓሉ ግርማ ያለበቂ ምክንያት መሞቱ ያሳዝነኛል፣ የሚል ሰው ሌሎች ንጹሃን ሰዎችን ያለበቂ ማስረጃ “የበዓሉ ገዳዮች” እያሉ መወንጀልም አግባብ አይደለም። ከወንጀሎች ሁሉ ወንጀል- ወንጀለኛ ያልሆነን ሰው “ወንጀለኛ” ማለት ነው! የበዓሉን ስም እየጠቀሱ “የበዓሉ ጠበቃ ነኝ” በማለት የበዓሉን ጉዳይ አስታኮ የግል ቂም መወጣጫና የፖለቲካ አጀንዳ ማስፈፀሚያ ለማድረግ መሞከር – በዓሉን እንደገና የመግደል ያክል ነው። በዚህ ቅኝት የተፃፉ ፅሁፎች በህዝቡ ውስጥ ሲሰራጩ የበዓሉን የአሟሟት ምስጢር የበለጠ ውሉን እያጠፋውና እያወሳሰበው ይመጣል የሚል ስጋት አለኝ። በዓሉ ግርማን በተመለከተ እስከአሁን ያልተመለሱ ጥያቄዎች ስላሉ እነሱ እስኪመለሱና የበዓሉ ግርማ መጨረሻ እስኪታወቅ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚችለውን ማድረግ አለበት። ይሄ ጥረት እንዲሳካ ከተፈለገ ከምንም አይነት ፖለቲካ ጋር ንክኪ የሌላቸው፣ ነፃና ገለልተኛ ሰዎች በተለይም የሀገራችንን ታሪካዊና ወቅታዊ ሁኔታ በትክክል የሚረዱ፣ ከቂምና ጥላቻ ነፃ የሆኑ ወጣት ምሁራኖች ማሳተፍ ያስፈልጋል። እዚህ ላይ ሁላችንም ልንረዳው የሚገባ አንድ ቁም ነገር ያለ ይመስለኛል።

እንደ አንድ መጠነኛ የስነጽሁፍ ግንዛቤ ያለው ተራ ዜጋ የጋዜጠኛ አበራን ያለፈ ታሪክ፣ የግለሰቡን ባህርይ፣ ድሮ የነበረውንና አሁን እያራመደ ያለውን የፖለቲካ አቋምና እንቅስቃሴ፣ ይህን ጽሁፍ ለምን አላማና ማን ልኮት ፃፈው የሚለውን የሰውዬው የግል ታሪክ ላይ ብዙ ጊዜ ሳላጠፋ የጽሁፉን ይዘት ብቻ ሚዛን ላይ አስቀምጬ ለማየት ሞከርኩ። ይኸው ጽሁፍ እንኳን እውነተኛውን የበዓሉ ግርማን አሟሟት ሊነግረን እራሱ በውሸት ስማቸውን ሊያጠፋቸው የፈለጋቸውንም ሰዎች ሰሩት የሚለውን የውሸት ወንጀል ሴራም በግልጽ የሚያሳይ አይደለም። ፅሀፊው ይህን ትልቅ አጀንዳ ያለውን ጽሁፍ ሲጽፍ በቂ ዝግጅት አላደረገም፣ አለኝ የሚለውን እውነት የሚያጠናክርለትም የተለየ ማስረጃ የለውም። የአበራ ጽሁፍ በልብወለድም ይሁን በኢልብወለድ መሰረታዊ የጽሁፍ ሚዛን ሲመዘን ደረጃውን ያልጠበቀ ተራ የፕሮፖጋንዳ ጽሁፍ ነው። ጽሁፉ በእውነተኛ መረጃ ድርቅ የተመታ በመሆኑ እንደ አጭር ልብወለድ መለካቱ የተሻለ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። የሚያሳዝነው ነገር ፅሁፍ እንደ ልብወለድ ቢወሰድ እንኳ ደካማ ከሚባሉት የልቦለድ ፅሁፎች የሚመደብ ነው፡:

ይሄ በዓሉን ለመግደል የተጠነሰሰ ሴራ የሚባለው ነገር ግልጽ ሆኖ ያልተቀመጠ እርስ በርሱ የሚጋጭ ነው። ለመሆኑ በአሉ ግርማን ለመግደል ይሄ ሁሉ ባለስልጣን የሚሳተፍበት ሴራ አስፈላጊ ነበር ወይ? ሴራው ቢኖርስ ይሄን ከፍተኛ የሀገሪቱ ባለስልጣናት የተሳተፉበትን ሴራ ተራው ጋዜጠኛ አበራ ለማ ለማውቅ እድሉና አጋጣሚው ነበረው ወይ? አበራ የሌሎች ሰዎችን ማስረጃ በመውሰድ እሱ ከሚያውቀው ነገር ጋር በማገናኘት መረጃ ትንተና ነው የሰጠው ቢባል እንኳ ለመሆኑ አበራ እንደምንጭ የተጠቀመበት መረጃ ምን ያክል እውነተኛ ነው? ይህን ያገኘውን መረጃ አበራ በትክክል ለመተርጎማና ለመትንተን ችሎታውና ፍላጎቱ አለው ወይ? የሚሉ ጥያቄዎች መነሳታቸው አይቀርም። በዚህ ጽሁፍ ውስጥ ብዙ የሚጠየቁ ጥያቄዎች፣ ብዙ ያልተመለሱ ነገሮች አሉት።

በኔ ግምት አንድ ቅን ዜጋ ይህን ጽሁፍ ሲያነብ መጀመሪያ አበራን የሚጠይቀው ጥያቄ “ለመሆኑ በደርግ ዘመን አንድ ደራሲ ለመግደል ይህ ያክል የተቀነባበረ ሴራ አስፈላጊ ነበር እንዴ?.” የሚል ነው። ጋዜጠኛ አበራ የደርግ ስርአትን ጠንቅቀው የሚያውቁ ንጹሃን ዜጎችን ያለምንም ምክንያት ያለምንም ሴራና አድማ በቀላሉ የመግደል ዘመቻው ውስጥ ተሳታፊ ስለነበሩ ጥያቄውን በቀላሉ ይመልሱታል። በነገራችን ላይ ጋዜጠኛ አበራ የቀይ ሽብር ነፍሰ ገዳዮች ጉዳይ የያዙት ልዩ አቃቤ ህግ ግርማ ዋቅጅራ ክስ ውስጥ እነማህደር የተባሉትን ወጣቶች በማስገደል ስማቸው በ27ኛ ተርታ ተመዝግቦአል። ከኢህአፓ መስራች አንዱ የሆኑትም ክፍሉ ታደሰ ደግሞ በመጽሃፋቸው ላይ አበራ ለማ ማስታወቂያ ሚ/ር አካባቢ በ07 ቀበሌ ቀንደኛ ነፍሰ ገዳይ እንደነበሩ ጠቅሰዋቸዋል። በአዲስ አበባ ከተማ የብዙ ወጣቶችን ደም የጠጣው የእርገጤ መድበው የቅርብ ጓደኛ እንደነበሩም የሚያውቋቸው ሁሉ ስለሚናገሩ በደርግ ጊዜ እንኳን እነኰ/ል መንግስቱ እነ አበራ እንኳን የሰዎችን ነፍስ በቀላሉ ማጥፋት የሚችሉበት ዘመን ስለነበረ የጋዜጠኛ/ደራሲ በዓሉ ግርማም ህይወት እንዲሁ በቀላሉ መቀጠፉን ለማሰብ አስቸጋሪ አይደለም።

ሌላው ይህን ጽሁፍ ተራ ውሸት የሚያደርገውና አጠቃላይ የጽሁፉን ይዘት የሚያናጋው በዓሉ ግርማ የተገደለው በተቀነባበረ ሴራ ነው ብሎ ሊነግረን የሚፈልገው ሃሳብ በግልጽ የተቀመጠ አለመሆኑ ነው፤ “ሴራውን” በጥንቃቄ ስንመረምረው ሁለት አይነት ይመስላል፤ በሴራው ውስጥ ማን ከማን ጋር ተባብሮ እንዳቀነባበረው በግልጽ አላስቀመጠውም። በጥንቃቄ ስላልዋሸ ሴራዎቹ የተለያዩና እርስ በርስ የሚቃረኑ ሆነውበታል። አንደኛው ሴራ መንግስቱ የተሳተፉበት ሆኖ ምንጩ ከላይ ይመስላል፤ አበራ በአጽሁፉ ገጽ 7 ላይ « ሊቀመንበር መንግስቱ በዘመነ ስልጣናቸው እነበዓሉ ግርማን ለማሰውገድ እነሙልጌታ ሉሌን ተጠቅመው» በዛው ገጽ ላይ በዓሉ ግርማ ለማጥፋት ከነኰ/ል መንግስቱ ጋር ከመሰጠሩ ጓደኞቹ ጋር ሙልጌታ ሉሌ አንዱ እንደሆነ በዚህ መጽሀፍ ገጽ 59 ላይ ይስተዋላል» ይለናል።

ሁለተኛው ሴራ የደርግ ባለስልጣኖች በዓሉን ለማስገደል ኰ/ል መንግስቱን ለማሳመን ያደረጉት ይመስላል። የዚህ ሴራ ምንጩ ከስር ይመስላል። በአላማም ሆነ በአቀናባሪዎቹ ማንነት ከአንደኛው ሴራ የተለየ ነው።ሁለተኛው ሴራ በአበራ ፅሁፍ ላይ እንደዚህ ተቀምጣል። « ኦሮማይ ብዙ በስልጣን ላይ ያሉ ሰዎችን ስለሚነካካ ብዙ ሰዎችን አስቆጥቷል….እንደተለመደው ሊያጠፉት የሚፈልጉ ሰዎች ተሰባሰቡና መከሩ፤ ሁሉም በየተራ መንግስቱ ጋር እየሄዱ አሉታዊ የሆኑ ነገሮችን እንዲነግሩት ተደርጐ በዓሉን የማጥፋቱ ሴራ ተቀነባበረ» ይሄ ሴራ መንግስቱን ብቻ ሳይሆን ጓደኞቹንም ለማሳመን ጥረት ተደርጓል፣ “የቅርብ ጓደኞቹን አሳመኑና” ይህ ሴራ የደርግ ባለስልጣናት መንግስቱን ለማሳመን በራሳቸው በመንግስቱ ላይ የተጠነሰሰ ሴራ ነው። ለበዓሉ ቅርብ የሆኑና ጓደኞቹን ጭምር አሳመኑና ሁሉም በየተራ መንግስቱ ጋር እየሄዱ ስለበዓሉ አሉታዊ የሆኑ ነገሮችን እንዲነግሩት ተደርጐ በዓሉን የማጥፋቱ ሴራ ተቀነባበረ፤ ኦሮማይ ማለት አለቀለት፣ አበቃለት ማለት እኮ ነው እያሉ መንግስቱን ጠመዘዙት፣ መንጌ ይህን አይወድም» እዚህ ላይ የሴራው ጠንሳሾች የደርግ ባለስልጣኖች ናቸው፤ አላማው መንግስቱን መጠምዘዝ ነው፤ በዚህ ሃሳብ መንግስቱ ስሜታዊ እንጂ ሴረኛ አይደሉም።
ስለ በአሉ ግርማ አሟሟት ከነገርከን ከነዚህ እርስ በርስ ከሚቃረኑ ሁለት ሴራዎች የትኛውን አምነን እንቀበልህ? የመጀመሪያውን ማለትም በመንግስቱና በጋዜጠኛ ሙልጌታ ሉሌ መካክል የተደረገውን? ወይስ በመጽሀፉ በተናደዱት የደርግ ባለስጣናት መካከል የተደረገውን ሁለተኛውን ሴራ? ለወደፊቱ እንዲህ አይነት ከባድ ውሸት ስትዋሽ ሰዎች ሊነቁብኝ ይችላሉ ብለህ መጠንቀቅ ጥሩ ነው። ለግዜው የመጀመሪያውን ሴራ ትክክል ነው ብለን እንውሰደው፤ ምክንያቱም ከመጀመሪያው ሴራ ተነስተህ የራስህ የሆነ ሌላ ሰዎችን የሚወነጅል ተከታታይ ታሪክ በጽሁፉ ውስጥ ስለጨመርክ።
ኰ/ል መንግስቱና ታዋቂው ጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ በአሉን ለማጥፋት በመንግስቱ አማካይነት ሴራ ተጠነሰሰ። መንግሥቱ በአሉን ማጥፋት ሲያቅታቸው ለሙልጌታ በአሉን እንድገድል ከረዳኸኝ የበአሉን ስልጣን እሰጥሃለሁ አሉት፤ ሙልጌታ የበአሉን ቦታ ይመኝ ስለነበር በሴራው ውስጥ (ለመንግስቱ ምን እንድሚረዳቸው ግልጽ አይደለም) ተሳተፈ፤ በኋላ መንግስቱ በአሉን ካስወገዱ በኋላ ለሙልጌታ የገቡትን ቃል ሳይፈጽሙ ቀሩ፤ በዚህ ምክንያት ሙልጌታ ሉሌ ቂም ይዞ ነበር፤ ኢህዴግ ሲገባ “አጥፍቶ መጥፋት” የሚል መጽሃፍ ፃፈባቸው፤ በዚህ ምክንያት በአሉን ለመግደል ያሴሩት ሰዎች ተጣሉ የሚል ለማመን የሚያስቸግር ቅዠት የሚመስል መላምት ቃላት በመቀጣጠልና በመቆራረጥ ሊፈጥር ይፈልጋል።
ለመሆኑ ኰ/ል መንግስቱ በአሉ ግርማን ለምን መግደል አስፈለጋቸው? በመጽሃፉ ውስጥ ስለ እርሳቸው ጥሩ ነገር ነው የጻፈው። እሺ መግደል ፈለጉ የሚለውን እንመን። በአሉን ለመግደል ኰ/ል መንግስቱ ከሌሎች ሰዎች ጋር ሴራ ማድረግ ለምን ያስፈልጋቸዋል? ሴራ ማድረግ ቢያስፈልጋቸው በሴራው ውስጥ እነሙሉጌታ ሉሌ ምን ይጠቅሟቸዋል? የሚሾሙት ራሳችው፣ የሚሽሩት ራሳቸው፣ የሚገድሉት ራሳቸው ሆነው ለመሆኑ መንግስቱ ሃ/ማርያም በአሉን ለማጥፋትና ሙልጌታ ሉሌን ለመሾም ምን ሴራና ምስጢር ያስፈልጋቸዋል? ይሄ አላግባብ የመንግስቱን መረን አልባ ስልጣን ማኰራመትና በአሉንና ጋዜጠኛ ሙልጌታን ስልጣን መለጠጥ ይመስለኛል። አበራ ይህን የመንግስቱንና ሙልጌታን ሴራ አገኘሁት የሚለው በአንድ ምንጭ ዙሪያ ጥምጥም ሄዶ ነው። ከቀድሞ አንድ የደርግ ባለስልጣናት ጋር ቃለመጠይቅ አድርጋለች የሚላት በእሱ አጠራር “መርማሪ ፀሐፊ” ገነት አየለ ናት። ጓድ ቁጥር 53 የሚል ኮድ ተሰጥቶታል። ስለዚህ ሰው ኋላ እመለስበታለሁ፡፤

ለጊዜው ይሄ ጓድ ቁጥር 53 እውነተኛ ሰው ነው (ፈለቀ ገድለጊዮርጊስ ነው) የተናገረውም እሱ ነው ብለን ብንቀበለው ይሄን ሃሳብ እንደተለመደው እርስ በርሱ ይጋጭል። መንግስቱ ሃ/ማርያም 17 ዓመት ሙሉ ብቻቸውን የፈለጉትን እየገደሉ፣ የፈለጉትን እየሾሙ፣ ያሻቸውን እያደረጉ የኖሩ ፈላጭ ቆራጭ መሪ ከነስማቸው “ቆራጡ መሪ” አንድ በአሉን ለማስወገድ ያውም ሌሎቹ የደርግ ባለስልጣናት ፍላጐት ተጨምሮበት ሴራ ውስጥ ገቡ በሴራው ምንም ጥቅም የሌላቸውን ግለሰቦች ሴራ ውስጥ አስገቡ ነው የሚለን። ይህን ሴራ አለ ብሎ ማሰቡ በተለይ ደግሞ ከዚህ ሴራ ተነስቶ በመንግስቱና ጋዜጠኛ ሙልጌታ መካከል ከበአሉ ሞት በኋላ መካካድና ጭቅጭቅ ተፈጠረ ብሎ ሌላ ሴራ ከአየር ላይ ዘግኖ ማምጣቱ ሞኝነት ነው፤ ይህን ሃሳብ ሰው ያምንልኛል ብሎ ማሰቡ እብደት ነው።

በመቶ ሺህ የሚቆጠር ሰራዊት የሚያዙ፣ የጥይትን እርሳስ እንደመፃፊያ እርሳስ የሚጠቀሙ ታላላቅ የጦር ጄኔራሎችን በአንድ ቁራጭ ወረቀት አዘው በአንድ ጀንበር የሚያስፈጁት ኰ/ል መንግስቱ ሃ/ማርያም በአሉ ግርማን ለማስገደል ከነሙልጌታ ሉሌ ጋር በማሴር ጊዜ ሲያጠፉ ነበር የሚል ታሪክ ጽፎ ማቅረብ የአንባቢውን ጊዜ ማጥፋት ይመስለኛል። በነገራችን ላይ “መርማሪዋ” ጋዜጠኛ ለሁለተኛ ጊዜ ባሳተመችው መጽሃፍ ላይ መንግስቱን ስለሙልጌታ ሉሌ አንስታባቸው ነበር፤ « እኔ ከርሱ ጋር ምንም ግንኙነት የለኝም፤ ከሱም ጋር ምሳ የበለሁበት ጊዜ የለም፤ ሾምነው ምን እንደሚፈልግ አላውቅም» ነው ያሉት።እና ገነት በመጀመሪያው መጽሃፍ ስለ ሁለቱ ሰዎች የነገረችንን በሁለተኛውም መጽሃፍ ኰ/ል መንግስቱ ያፈርሱታል። በርግጥ ታዋቂው ጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ “አጥፍቶ መጥፋት” የሚል መፅሀፍ ጽፎ መንግስቱን በስልጣን ዘመን ያጠፉትን ጥፋት በዛ ልዩ የጽሁፍ ችሎታው በማስቀመጡ ደስተኛ እንዳልነበሩ ይታወቃል። ይሄን ቅሬታ ወስዶ ከበአሉ ሞት ጋር በማገናኘት ሴራ መፍጠር የአበራን ሴረኛነት ነው የሚያሳየን።

ከኰ/ል መንግስቱና ከጋዜጠኛ ሙልጌታ ሉሌ ሴራ ሳልወጣና ወደ ሌላ ሃሳብ ሳልሄድ የአበራ የፈጠራ ሴራ አንድ ነገር ልበል፤ ጓድ ቁጥር 53 ይኑር አይኑር የማይታወቀው የደርግ “ቱባ” ባለስልጣን የሰውን ፍላጐት የማንበብ ልዩ የነብይነት ፀጋውን ተጠቅሞ ይሁን እራሱ ጋዜጠኛ ሙልጌታ ሉሌ ነገሮት እንደሆነ ሳይገልጽልን ጋዜጠኛ ሙልጌታ ሉሌ ለምን የበአሉ ማስገደል ሴራ ውስጥ እንደገባ የሚያሳይ በቀጥታ ሳይሆን በተዘዋዋሪ አንባቢ እንዲያስብ ተደርጐ የተሳለ አንድ አረፍተ ነገር አለ። “የበአሉን ቦታ ይመኝ እንደነበረ አውቃለሁ” በአበራ ጽሁፍ ገጽ 6 ላይ በገነት መፅሃፍ ገጽ 59 ላይ ይገኛል።
የአበራ ለማ ዋና አጀንዳ ታዋቂወን ጋዜጠኛ ሙልጌታ ሉሌን የበአሉ ግርማ ሞት ላይ እጁ እንዳለ በማስመሰል ያለ የሌለ እውቀቱንና አረፈተ ነገር የመቀጣጠልና የመቆራረጥ ጥበቡን ይጠቀማል። እንዳለመታደል ሆኖ ዓ/ነገርን ቆራርጦና ቀጣጥሎ ሊነገረን የፈለገው ሙልጌታ ሴራ ውስጥ የነበረው የበአሉን ቦታ ፈልጐ ነው የሚለውን ሃሳብ ሙሉ በሙሉ ውሸት የሚያደርግ እርስ በርሱ የሚቃረን ሌላ መረጃ አስቀምጧአል።

አበራ በጽሁፉ መጀመሪያ በዓሉ የሞተበትን ቀን የካቲት 24 1976 ዓ.ም ነው፤ በ3ኛው ገፅ የመጨረሻው አንቀጽ ላይ ኰ/ል መንግስቱ በዓሉ ግርማ በመጽሃፉ ምክንያት ከስራ እንደተባረረ ይነግሩናል። በአሉን ከስራ ያሰናበቱት ቀን ኰ/ል መንግስቱ እንዲህ አሉት “ባለህበት የሃላፊነት ቦታ የምትቆይበት ሁኔታ ሊኖር አይችልም” ብለው ጳጉሜ 5 ላይ ከስራ አሰናብተውታል። በሌላ አገላለጽ በዓሉ በመፅሃፉ ምክንያት ከመገደሉ ከ6ወር በፊት ከስራ ተባሮአል፤ የኔ ጥያቄ ሙልጌታ ሉሌ ከስራ ከተባረረ 6ወር ያለፈውን ጓደኛውን ቦታ ለመያዝ ጓደኛውን አስገደለው የሚል ነገር መናገር ለሰው ምን ትርጉም ይሰጣል?
አበራ የበአሉ አሟሟት ሴራ (የተነሳበትን ሃሳብ) ያጠናክርልኛል ብሎ በዋና የመረጃ ምንጭነት የሚጠቅሳቸው ሶስት ሴቶችን ነው። አንደኛ- የጋዜጠኛና ደራሲ በዓሉ ግርማ ባለቤት ወ/ሮ አልማዝን፣ የበዓሉን ሴት ልጅ ወ/ሮ መስከረም እንዲሁም ስለበዓሉ ጉዳይ ከወ/ሮ መስከረም ኢሜል ውጭ ሁለቱ ጽሁፎች አገር ሁሉ የሚያውቃቸውና 10 አመት ያለፋቸው ታሪኮች ናቸው። የወ/ሮ መስከረም ኢሜልም ስለበዓሉ አሟሟት ፍንጭ አይሰጥም። ጋዜጠኛ አበራ ለማ ከበዓሉ ግርማ ቤተሰቦች ጋር የተለየ ቅርበት ስላለው ያገኘው መረጃ አስመስሎ ያቀረበው የመጀመሪያው ማስረጃ የደራሲ በዓሉ ባለቤት ወ/ሮ አልማዝ በዓሉ ስለመጥፋቱ ደራሲ አስፋው ዳምጤ ያውቃል ብለው በኢህአዴግ ዘመን ለጠቅላይ አቃቤ ህግ ያቀረቡትና ውድቅ የተደረገው ክስ ነው። ሌላው ጋዜጠኛ አበራ ለማ “መርማሪ ፀሃፊ” እያለ የሚያደንቃት ገነት አየለ የመንግስቱ ሃ/ማርያም ትዝታዎች ብላ ያወጣችው መፅሃፍ ላይ ስለበዓሉ የተጠየቁ ጥያቄዎችንና መልሶችን መስረት አድርጐ ነው (በዚህ መፅሀፍ ገፅ59 ላይ የተጠቀሰው ቁጥር53 የሚባል የፈጠራ ሰው በውል ይኑር አይኑር ያለየለት የፈጠራ ሰው የሚመስል ሰው የተናገረው ነገር የሃሳቡ ማጠናከሪያ መሆኑ ነው)
ፀሀፊ ገነት አየለ የበዓሉ ግርማን አሟሟት በተመለከተ ሶስት የደርግ ከፍተኛ ባለስልጣኖችን አግኝታ 5 ጥያቄዎችን ብቻ ጠይቃለች። አራቱ ጥያቄዎች « በዓሉ ማን ገደለው?» የሚል ተመሳሳይ ጥያቄ ሲሆን አንዱ ደግሞ በጋዜጠኛ አበራ አገላለጽ “መርማሪዋ ጋዜጠኛ” ኰሎኔል መንግስቱን “አፋጠጠቻቸው” የተባለለት “በዓሉ መፅሃፍ እንዲጽፍ አዘውታል?” የሚለው ነበር። አበራ የዚህን ጥያቄና እነኰ/ል መንግስቱ የሰጡትን መልስ መሰረት አድርጐ ነው በዋነኛነት ጽሁፉን የሚጽፈው። መርማሪ የተባለችው ጋዜጠኛ ሶስት የደርግ ባለስልጣኖችን አግኝታ የበዓሉን ግድያ ምስጢር እስከወዲያኛው የሚፈቱ መቶ ጥያቄዎችን መጠየቅ ሲገባት አንድ ጥያቄ ብቻ ሰንዝራ እድሉ እንዲያመልጥ ማድረጓ ያሳዝናል።

መቸም ገነት አየለ በተፈጠረላት አጋጣሚ የደርግ ባለስልጣናትን ስለበዓሉ ጉዳይ መጠየቋ የሚደነቅ ቢሆንም ነገር ግን መርማሪ ጋዜጠኛ (ኢንቬስቲጌቲቭ ጆርናሊስት) የሚለው ስም የሚበዛባትና ጨርሶ ያልነካቸው መሆኑ ሳልገልጽ አላልፍም። አንድ መርማሪ ፀሃፊ ስለሚጠይቀው ነገር በሚገባ የተዘጋጀ፣ የውስጥ መረጃ ያለው መሆን አለበት። መርማሪ ጋዜጠኛ የተባለችው ገነት ግን ምንም አይነት መረጃ እንደሌላት የሚያስታውቀው በአበራ ጽሁፍ ገፅ 3 እንዲሁም በገነት መጽሀፍ ገጽ212 ላይ ያነሳችውን ጥያቄ ስናይ ነው። « ስለዚህ እርስዎ ቀይ ኮከብን በተመለከተ በዓሉ ግርማን መፅሀፍ ፃፍ ብለውታል የሚባለው እውነት ነዋ?» ይላል። ከዚህ ይልቅ “ የበዓሉ መፅሀፍ ኦሮማይ ከመታተሙ በፊት አንብበው እንዲታተም ፈቅደውለት ነበር ወይ?” ተብሎ ጥያቄው ቢቀርብ ኖሮ እንቆቅልሹ ይፈታ ነበር። ለነገሩ ወ/ሮ ገነት ያችኑ ጥያቄ ጠይቃ ተጠያቂው አላስፈላጊ ነገር እንዲያወሩ እድል መስጠት እንጂ- ተከታታይ ጥያቄ (ፎሎው ኦፍ ኮዌስችን) አላቀረበችም። በመሆኑም ጋዜጠኛ አበራ የጋዜጠኛ ገነትን ተልካሻ ጥያቄ መሰረት አድርጐ እጅግ ደፋር ድምዳሜ ላይ መድረሱ አሳፋሪ ነው።

ጋዜጠኛ አበራ ለማ የፅሁፉ ዋና አጀንዳ አድርጐ የተነሳው ገነት አየለ አግኝታ ጠየቀችው ከሚባለው ከሶስቱ የደርግ ባለስልጣኖች አንዱ የሆነውና ስሙ ያልተጠቀሰው “ጓድ ቁጥር 53” የሚባለው ግለሰብ ነው። ይሄ ጓድ ቁጥር 53 በእውን በገሃዱ አለም ያለ ሰው ነው..ወይስ የገነት የፈጠራ ውጤት?..የሚል ጥያቄ ለማንሳት የግድ ጋዜጠኛ ገነት አየለን መሆን አያስፈልግም። ሰውየው እንደተባለው እውነተኛና ያለ ሰው ነው ከተባለ “የበዓሉ ግርማን አሟሟት አውቃለሁ፣ እነሙልጌታ ሉሌ አሉበት” እያለ የሰው ስም እያጠፋ በአንፃሩ የራሱን ስም መደበቁ በጭራሽ ተቀባይነት የለውም። ትክክልም አይደለም። ለበዓሉም፣ ለሚከሰስትም ሰዎች፣ ለደራሲ በዓሉ ቤተሰቦችና ለኢትዮጵያ ህዝብ ሲል አውቃለሁ የሚለውን አደባባይ ወጥቶ ይናገር። ( ለነገሩ ጓድ ቀጥር 53 ስለበዓሉ አሟሟት አውቃለሁ የሚለውን ነገር ለመናገር ድፍረት አግኝቶ ከወጣ በገነት አየለ መጽሀፍ ገጽ 59 ላይ የቀባጠረው ብዙ ነገር ስላለ ለሱ ጥያቄ መልስ ሊያዘጋጅ ይገባዋል) በህግም ቢሆን ገድሎአል ብሎ የከሰሰው ሰው እንጂ ገድለሃል የተባለው ሰው አለመግደሉን የሚያሳይ ማስረጃ ማምጣት አይጠበቅበትም። ስለዚህ በአሉን የበሉት ጅቦች ሳይሆን በአሉን የበሉትን ጅቦች አውቃለሁ የሚለው ሰው የግድ ወጥቶ መናገር አለበት።

የጋዜጠኛ አበራን ጽሁፍ በዓሉ ግርማን ለማስገደል በኰ/ል መንግስቱ ሃ/ማርያምና በሌሎች ታላላቅ የደርግ ባለስልጣኖች እንዲሁም የበዓሉ የቅርብ ጓደኞች፣ ጋዜጠኞችና የማስታወቂያ ሚ/ር ባለስልጣኖች መካከል የተደረገውን ሴራ ሊነግረን ይሞክራል። ከላይ በገለጽኩት መንገድ ህዝብ የሚያውቃቸውን መረጃዎችንና የመረጃ ምንጮችን መሰረት አድርጐ እንደ አዲስ ክስተት ሊነገረን ይሞክራል። ታዋቂው አልበርት አንስታይን “እብደት ማለት አንድን ተመሳሳይ ነገር እየደጋገሙ፣ እያደረጉ የተለየ ውጤት/ አዲስ ነገር መጠበቅ ነው” ይላል። በርግጥ ይሄ ምሳሌ የሚመለከተው በቅንነት – ስህተት ለሚሰሩ የዋሆች እንጂ ለጋዜጠኛ አበራ ለማ አይነቱ ሆን ብሎ ለሚያጠፋ ወይም የተለየ ተልእኮ ላለው ሰው አይደለም። አበራ አምነን እንድንቀበለው የሚፈለገው ሴራ በእውነት ላይ ያልተመሰረተ፣ ለአመታት ሲወሩ ከነበሩት ነገሮች የተለየ አዲስ ነገር የሌለው፣ የመረጃ ምንጮቹ ያልተቀየሩና በስነፅሁፍ ሚዛን ተራ የሚባል ነው። ይሄ ጽሁፍ ለበዓሉ ግርማ ታዝኖና ታስቦም የተፃፈ አይደለም። ብዙ ተራ ስድቦች የሚበዙበት ነው። ሆን ተብሎ በዓሉ ግርማን “አስገደሉ” የሚላቸውን ሰዎች ብቻ ሳይሆን የራሱን የበዓሉን ስም ጥላሸት ለመቀባትና ህዝቡን ለማሳሳት (ግራ ለማጋባት) በተፈጠሩ የውሸት ታሪኮች የታጨቀና የተንሻፈፉ መላምቶች የሚበዙበት፣ በጣም አደገኛ የክርክር ግድፈቶች ያሉት፣ አሰልቺ ቃላቶችና አረፍተ ነገሮች የሚበዙበት፣ ግማሽ እውነቶች በተደጋጋሚ የሚጠቀም ተራ የፕሮፖጋንዳ ፅሁፍ ነው።

በመግቢያዬ ላይ እንደገለጽኩት የጋዜጠኛ አበራ ጽሁፍ አራት ክፍሎች አሉት። የመጀመሪያው ገጽ በበአሉ ሞት እጁ አለበት የሚለውን ደራሲ አስፋው ዳምጤ ይከሳል። ከገጽ2 እስከ 5 ደግሞ “ታላላቅ” ጅቦች የሚላቸውን የደርግ ባለስልጣናት ይከሳል። ከገፅ 5 እስከ 9 ታዋቂውንና አዋቂውን ጋዜጠኛና የብእር አርበኛ የሙልጌታን ሉሌ ስም ያጠፋል። ከገጽ 10 በኋላ ደግሞ “የማስታወቂያና መርሀ ብሄር ሚ/ር ካነሳን ዘንዳ ወደኋላ ዘመን ተመልሰን የጓዳ ምስጢር ሰነድ መፈተሽ የግድ ሊለን ነው” ብሎ በደርግ ዘመን ብቻ ሳይሆን በአጼ ሃ/ስላሴ ዘመን ሁሉ የተከበረውን ታዋቂውን ጋዜጠኛ የገዳሙ አብርሃን ስም ጥላሸት ለመቀባት ይፈለጋል።

በርግጥ አበራ ለማ ይሄ ምኞቱ ብዙ የተሳካለት አይመስልም። አንድ ስለ ኢትዮጵያ መጠነኛ ግንዛቤ ያለው ሰው የአበራን ጽሁፍ ሲያነብ የነዚህን ሰዎች ጥፋት ሳይሆን የአበራ ለማን አጭበርባሪነት ውሸታምነት በተራ ምክንያት ሰዎችን ለማታለል የሚሞክር አላዋቂ ሰውነት ግልጽ አድርጐ ያሳያል። ይሄ ጽሁፍ እንኳን ወንጀለኛ ናቸው ያላቸውን ሰዎች ይቅርና እየታገልኩለት ነው የሚለውን የደራሲ በአሉ ግርማን ገጽታ የሚያበላሽ ሰላማዊውና ተወዳጁ በአሉ ግርማን ባለብዙ ጠላት የሚያደርግ ጽሁፍ ነው።

ስለ በአሉ ግርማ አሟሟት አጣራች የሚላትን ገነት አየለን ቃለምልልስ ዋቢ አድርጐ የሚነሳው የአበራ ለማ ጽሁፍ በአሉ ግርማን የደህንነት ሰራተኛ ያደርግዋል። አበራ ገነት ስለ በአሉ ቃለመጠይቅ ካደረገችላቸው ሰዎች አንዱ የቀድሞ የደህንነት ዋና ሰው ተስፋዬ ወ/ስላሴ ናቸው ይላል፤ በአበራ ጽሁፍ በአሉ ግርማ ከስራ ባልደረቦቹ ጋር ችግር እንዳለበት ተስፋዬ ወ/ስላሴ ጠቁመውኛል ብሎ ተስፋዬ ወ/ስላሴ ስለበአሉ ለገነት ነግሮት የሚለውን ሀሳብ በራሱ በአበራ ፅሁፍ ገጽ 5 ላይ እንዲህ አስቀምጦታል፤

« በዓሉ መቼም በዚህ መጽሀፉ ብቻ ሳይሆን በሌላ በሌላም..ከእኛ ጋር በመስራቱም ሁሉ ብዙ ሰዎች ጠምደውታል…የስራ ባልደረቦቹም ቅርበት በመፍጠሩ ጥላቻ አላቸው» ይልና እንደአበራ አባባል ይህን ሃሳብ የተጠቀመበት በአሉ ከስራ ባልደረቦቹ ጋር ችግር አለበት ለማለት እንዲመቸው ነበር፤ ጽሁፉ ግን በአሉ ግርማ የደህንነት ሰው ነበር ነው የሚለን። በርግጥ አበራ ቃላት የመቆራረጥና የመቀጠል የሞኝ ዘዴውን በመጠቀም ከዚህብ አረፍተ ነገር “ ቅርበት በመፍጠሩ ጥላቻ አላቸው” የሚለውን በሚቀጥለው ገጽ ቆርጦ ወስዶ የበአሉን ጓደኞች ሊወነጅልበት ነበር። በአሉን ብዙ ጠላት አለው የደህንነት ሰው ነው ብቻ ሳይሆን የሚለው በመጽሃፉ የሚያውቃቸውን ሰዎች ገፅባህርይ አድርጐ መሳደብ የሚወድ ሰው ነው ይለናል፡፤

“በአሉ ግርማ በ1972 ዓ.ም ባሳተመው “የቀይ ኮከብ ጥሪ” ታሪካዊ ልብ ወለድ መጽሃፍ ላይ ከዋናው ሚ/ር እስከ ተራ ሪፖርተሮች ያሉትን የማ/ሚ/ር ሰራተኞች በገፀ ባህርይነት እየተጠቀመባቸው ደህና አድርጐ ተሳልቆባቸዋል። ከነዚህ በገፀ ባህርይነት ከተሳለቀባቸው መካከል ገዳሙ አብርሃ ነው” ይለናል። በሱ ቤት ስለበአሉ ደህና ነገር ማውራቱ ነው፤ ለሌላ አንባቢ የሚሰጠው ትርጉም በ1972 የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች ላይ ተሳለቀ፣ በ1974 መጽሃፉ ላይ ደግሞ ስለደርግ ባለስልጣናት ሲሳለቅ አደገኛ ወጥመድ ውስጥ ገባ የሚል ትርጉም ነው የሚሰጠው።
በአሉን በማስገደል ሴራ ላይ እጁ አለበት ብሎ በመጀመሪያው ገፅ ላይ ያቀረበው አስፋው ዳምጤን በተመለከተ ብዙ ውሸቶች የተንሻፈፉ መላ ምቶች፣ የአንድ ወገን እውነቶች ይበዙበታል። በነገራችን ላይ ስለአስፋው ዳምጤ ወንጀለኛነት አበራ የፃፈው አበራ የጋዜጠኞች ማህበር ሊቀመንበር ለመሆን ፈልጐ እሱና ማሞ ውድነህ ስለተቃወሙት ነው ይባላል፣ ለጊዜው እኔም እንደሱ አሉሽ..አሉሽን ትቼ ወደዋናው ይዘት ላይ ብቻ ላተኩር።

አበራ ስለአስፋው ዳምጤ ወንጀለኛነት የሚጠቅሰው ማስረጃ የበአሉ ግርማ ባለቤት በኢህዴግ ዘመን በአሉ በሞተበት ቀን አስፋው ደውሎለት ነበር፤ በአሉም ከቤት ወጥቶ የቀረው አስፋው ጋር ልሂድ ብሎ ነው፤ ብለው ለአቃቤ ህግ ያመለከቱትና ውድቅ የሆነ ክስ መሰረት አድርጐ ነው፤ ስለበአሉ አሟሟት የተለየ ሴራ አለ እስከተባለ ድረስ ያንኑ ነገር ነው ደግመን የምንጠይቀው ለመሆኑ በደርግ ዘመን ደርጐች በአሉን መግደል ከፈለጉ አስፋው ዳምጤን ከቤት ይዘህልን ውጣ ይሉታል ወይ? ይዘህ ውጣ ቢባል መልሱ ምን ነበር የሚሆነው? ግምቴ ስህተት ሊሆን ይችላል፤ ግን እንደኔ ግምት በዛ ዘመን ደርጐች በአሉን ከፈለጉት ራስህ ና ቢሉት በአሉ እንቢ አይልም፤እንኳን እሱ ባለቤቱም ይዘውት ይምጡ ቢሉዋቸው የተለየ መልስ ያላቸው አይመስለኝም፤ በተለይ አበራ በአሉን ይዘህ ና ብለው እነመንግስቱ ቢያዙት ገና እነሱ ጋር ሳይደርስ እራሱ ገድሎት ሬሳውን ይዞ የሚመጣ ነው የሚመስለኝ፤
አበራ የወ/ሮ አልማዝን ክስ መሰረት አድርጐ የራሱን ሴራ የሚያጠናክርበትና አስፋው ዳምጤን የሚከስበት ታሪክ ይፈጥራል፤ አንደኛ አስፋው ዳምጤ በአሉ ከሞተ በኋላ በዚያው ጠፋ፣ እባሉም ቤት ሄዶ አያውቅም፣ ስልክም ደውሎ አያውቅም ይሄ የሆነው ደግሞ የጥፋተኝነት ስሜት ስለሚሰማው ነው፤ ለማለት የመፅሃፍ ቅዱስ ጥቅስ ይጠቅሳል። ለዚህ የውሸት ክስ አሁንም አስፋው ዳምጤን በቅርብ ከሚያውቁ ሰው የሰማሁት ወ/ሮ አልማዝና ደራሲ አስፋው ዳምጤ በበአሉ ጉዳይ ተገናኝተው አውርተዋል፤ በመሃላቸው የተፈጠረ ቅሬታ አለ፤ እሱን ደግሞ አስፋው ዳምጤ እንደ አበራ ለማ ስላልሆኑ እውነቱን እንደ ጥላሁን ገሰሰ ሆድ ይፍጀው ብለው ዝም የሚሉ ይመስለኛል፤ ህዝብ ይወቀው ብለው የራሳቸውን እውነት ቢያወሩ ጥሩ ነው፤

ሌላው አበራ ለማ አስፋው ዳምጤን ወንጀለኛ ነው ብለን እንድናምን በገጽ 2 የመጀመሪያው አንቀጽ ላይ “በአሉ ግርማ እንደወጣ በቀረበት ሰሞን ከገንዘብ ሚ/ር ቋሚ ተጠሪነት ስራው ተባሮ…በድንገት የኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ ሆኖ በደርግ ተሾመ” ይልና ይሄ ሴራ አስፋው በአሉን አስገድሎ ተሾመ ነው መልክቱ፤ ይሄ ደግሞ ግማሽ ውነት ይባላል፤ አስፋው ዳምጤ ከደርግ ዝመን በፊት ከታወቀው ካምብሪጅ ዩኒቭርሲቲ የኢኮኖሚክስ ማስተርስ የነበረው በደርግ ጊዜ ልክ እንደ ጓደኛው እንደበአሉ ግርማ የገንዘብ ሚ/ር ቋሚ ተጠሪ (ሚኒስትር) የነበረ፣ ደርግ ጋር ስላልተጣጣመ ስራ የለቀቀ ሰው በአሉን አስገድሎ እዚህ ግባ የማትባል ድርጅት ም/ስራ አስኪያጅ ሆነ ነውየምትለን አቶ አበራ? ሰው ባታፍር እንኳ ፈጣሪን ፍራ::

አበራ በጽሁፉ ውስጥ ከገጽ 2-5 ገነት አየለ ከደርግ ባለስልጣናት ጋር ያደረገችውን ቃለመጠይቅና የነሱ መልስ ነው፤ ከላይ እንደጠቀስኩት ገነት አየለ በአሉን በተመለከተ በቂ ጥያቄ ስላልጠየቀች ከዛ ተነስቶ ምንም ማለት ባይቻልም በኔ አመለካከት አበራ በሚነግረን ሴራ መንግስቱና ሙልጌታ ሉሌ አሲረውም ይሁን ታናናሾቹ የደርግ ባለስልጣኖች ነገር እየሸረቡ እናዶዋቸው በአሉን ከገደሉ በህግ ባይቻል በታሪክ ተጠያቂ ናቸው፤ መንግስቱ ብ ዙ ሰው ገድለዋልና በአሉንም ገድለውታል ወይም እጃቸው አለበት ብሎ ካለጥፋታቸው መክሰስ አስፈላጊ አይመስለኝም፤፡

በአሉ ግርማ ተገደለ ተብሎ በደርግ ባለስልጣናት ዙሪያ እንደዘበት የሚወራው እውነት አሁን አበራ ወይም ገነት እንደምትነግረን አይነት አይደለም፤ ሌላ የተለየ ታሪክ ነው፤ እጃቸው አለበት የሚባሉትም ሰዎች ሌሎች ናቸው፤ የበአሉ ጉዳይ የቤተሰቡና የጓደኞቹ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ታሪክ ስለሆነ ሁላችንንም ይመለከተናል፤ አሁን ሁሉም ነገር አልፎ ታሪክ ሆኗል፤ ግን እውነተኛው ታሪክ ለኛና ለልጆቻችን ግልጽ ቢሆን የዘወትር ምኞታችን ነው፤ ስለበአሉ አገዳደል ትክክለኛው መረጃ ያላችሁ ባለስልጣኖች፣ ግለሰቦች ይህን በመስራት ታሪካዊ ግዴታችሁን ልትወጡ ይገባል።
በነገራችን ላይ ጓድ ቁጥር 53 የገነት መፅሀፍ በገጽ 59 በአበራ ጽሁፍ ገጽ 6 ላይ የተጠቀሰ በነአበራ አገላለጽ የደርግ ባለስልጣን ነው ይባላል፤ አንባቢዎች ጊዜ ካላችሁ አንድ ገጽ ብቻ ስለሆነች አንብቧት፤ በጣም የሚገርመው ለማመን የሚያስቸግሩ ሃሳቦች አሉት፣ እና ከዚህ ሰው ንግግር ተነስቶ ሰውን ወንጀለኛ ማለት በጣም ያሳዝናል።ጓድ ቁጥር 53 በኔ እይታ የበአሉ ግርማና የሙልጌት ሉሌ አለቃ ሳይሆን የነፍስ አባት ይመስላል፤ እነሱ የማይነግሩት ነገር የለም በዛ ላይ አይምሮ የሚያነብ ተሰጥኦም አለው።

ገና በጽሁፉ መጀመሪያ ጓድ ቁጥር 53 እንዲህ ይላል« መንግስቱ በአሉ ግርማን ቀይ ኮከብ መጽሀፍ እንዲጽፍ ይጠይቀዋል፤ ራሱ ፃፍ ማለቱን ማንም ሰው አያውቅም» ማንም ሰው ካላወቀ ጓድ ቁጥር 53 እንዴት አወቀ? « መንግስቱ ከሲዳሞ ጉብኝት ሲመለስ ኦሮማይን እያነበበ ነው የመጣው» ይለናል፤ መንግስቱ ደግሞ በአበራ ፅሁፍ ገጽ 3 ላይ “መጽሃፉን ማታ ማታ ነው ያነበብኩት 1 ሳምንት ፈጀበኝ” ይላሉ፤ ጓድ ቁጥር 53 “እንደተለመደው ሊያጠፉት የሚፈልጉ ሰዎች ተሰበሰቡና መከሩ፣ ለበአሉ ቅርብ የሆኑ ጓደኞቹ ጭምር አሳመኑ” እንደተለመደው ሊያጠፉት የሚፈልጉት እነማን ናቸው?

“ሙልጌታ ሉሌ ለደህንነት ይሰራል” ደህንነት የምስጢር ስራ ነው፤ “የበአሉን ቦታ ይመኝ እንደነበረ አውቃለሁ” ይህን ነገር ያወቀው በዛ የሰውን አይምሮ በማንበብ ችሎታው ተጠቅሞ ነው የሚል ጥያቄ ያስነሳል፤ የጓድ ቁጥር 53 ሌላ አስቂኝ ነገር ይነግረናል፤ መንግስቱ በአሉን ለመግደል ከሙልጌታ ጋር ሊያሴሩ ሲፈልጉ ሙልጌታን በቀጥታ ማግኘት ሲችሉ፤ሽመልስ ለጓድ ቁጥር 53 ፣ ጓድ ቁጥር 53 ለሙልጌታ ነገሩት ይለናል፤ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌን ጠርቶ ማሴርፈለገ በቀጥታ ደውሎ መጥራት ሲቻል ይሄ ሁሉ መዞር ለምን አስፈለገ? ገድ ቁጥር 53 ሌላ የሚቀባጥረው ነገር አለው ፤ ሙልጌታ ሉሌ መንግስቱ ጋር ሄዶ በአሉን ለመግደል በምስጢር ካሴሩ በኋላ ጓድ ቁጥር 53ን ፈልገው እኔና መንግስቱ በአሉን ለመግደል አሴርን ሊሉት ፈለጉ ጓድ ቁጥር 53 ምንም ነገር ሳይሰማ አእምሮው የማንበብ ችሎታውን በመጠቀም የሁለቱን ሰዎች ምስጢር ስለደረሰበት ለራሱ ለበአሉ ንገረው አልኩት ይለናል።

ጓድ ቁጥር 53 ምን ያህል ሞኝ ናቸው ሙልጌታን ያህል የአለምን የኢትዮጵያን ፖለቲካና ኢኮኖሚ ታሪክ ጠንቅቆ የሚያውቅ ምሁር በቀን አንድ መጽሃፍ የሚያነብ ፈላስፋ በ50 አመት የጋዜጠኛነት ሙያ ብዙ የኖረ ሰው ሰው ለመግደል ከመንግስቱ ጋር አሲሮ ለአለቃው/ለነፍስ አባቱ ሊነግረው ፈለገ፣ ነፍስ አባቱ ግን የነብይነት ችሎታውን ተጠቅሞ ይህንን ሴራ ቀድሞ አውቆ አልሰማ አለ፤ ጓድ ቁጥር 53 ፈለቀ ገ/ጊዮርጊስ ይሁን ከነብያቶቹ አንዱ መጥቶ እርሱን ለህዝብ መግልጽ ያለበት ይመስለኛል።

ጓድ ቁጥር 53 የራሱን ስም ደብቆ እየቀባጠረ የሰው ስም ካጠፋ በኋላ ስሙ የጠፋው ሰው ወጥቶ ይናገር እንኳን ሙልጌታ ሉሌ ሌላም ሞኝ ሰው የሚቀበለው አይደለም፤ ሙልጌታ ሉሌ ለውነት የቆመ፣ ከማያለቀው እውቀቱ ትውልዱን የሚያስተምር፣ የህዝብ አስተማሪ፣ የኢህዴግን መንግስት ገና ከመጀመሪያው በጽኑ የሚቃወምና የሚታገል የብዕር አርበኛ ነው። በአፄ ምኒልክ ዘመን ጋዜጠኛ የነበሩ ደስታ ምትኬን ጨምሮ እስከአሁኖቹ በዘመናችን ጋዜጠኞች እንደአርአያ የሚታይ ሰው ወያኔን የሚቃወምና የተጣመሙ የሃገራችን ታሪኮችን ጻፍክ ተብሎ ስሙን ማጥፋቱ ትክክል ነው ብዬ አላምንም። ሙልጌታ ሉሌ አሁንም ይጽፋል፣ አሁንም ትውልዱን ስለምንወዳት ኢትዮጵያ ያስተምራል፣ ስለ ዲሞክራሲ ይሰብካል፤ ስለ ጀግንነት ይናገራል። ትልቁን ሰው ማዋረድ ትንሹን ትልቅ አያደርገውም።

ጸጋዬ ገ/መድህንና ሙልጌታ ሉሌ በአንድ አካባቢ ያደጉ ብቻ ሳይሆን የአንድ ዘመን ሰዎች ናቸው። ከሙያቸው ጋር በተገናኘ አላስፈላጊ እስጥ አገባ አጋጥሟቸው ነበር። ሁለቱም ለተነሱባቸው ሰዎች የሰጧቸው ምላሾች ተመሳሳይና ሁል ጊዜ የሚጠቀሱ ናቸው። ጸጋዬ ገ/መድህን የሆኑ ሰዎች ተነስተውንብሃል በየጋዜጣው ስምህን ያጠፉታል፣ ለምን መልስ አትሰጥም ተብሎ ተጠየቀ። ጽጋዬም እነዚህ ሰዎች የትልቅ ሰው እግር ይዘው ሽቅብ መሳብ የሚሹ ናቸው፡ እኔ ደግሞ ለነኚህ ግልገሎች እግሬን አለሰጥም አለ፡፤ ሙልጌታ ሉሌም በጣም የምትወደውን የቅርብ ጓደኛህን በአሉ ግርንማን በማስገደል ሴራ ውስጥ አለህበት ብለው ሰዎች ስምህን ያጠፉታል፤ ለምን መልስ አትሰጣቸውም ተብሎ ሲጠየቅ እንዲህ ሲል መለሰ፣ በድሮ ጊዜ አንድ ሰው መኪና እየነዱ ሲሄዱ መንገድ ላይ ሰው ገጩ የገጩት ሰው ትንሽ ጠቆር ያለ በዛን ጊዜ አጠራር “ባርያ” ስለነበረ እኔ ከሱ ጋር አልነጋገርም፣ ጌታውን ጥሩልኝ አሉ። እኔም ስለዚህ ነገር መልስ ል፤እመስጠት ወይ ጓድ ቁጥር 53 ራሱን ገልጦ ይምጣ፣ ካልሆነም አበራን የላኩት ጌቶች ይታወቁና ለነሱ መልስ እሰጣለሁ አለ።
ጋዜጠኛ አበራ ከገጽ 10 ጀምሮ እስከ ጽሁፉ መጨረሻ ገጽ 16 ድረስ የፃፈው እሱ ጋዜጠና ሆኖ በሰራበት ዘመን በማ/ሚ/ር ውስጥ የነበሩ የጓዳ ምስጢሮችን የሚላቸውን ነው፤ “የማ/ሚ/ር መስሪያ ቤት ካነሳን ወደ ኋላ ተመልሰን የጓዳ ምስጢር ሰነድ መፈተሽ የግድ ነው” ይለናል፤ በዚህም መሰረት አበራ በዚህ መስሪያ ቤት ይሰሩ የነበሩ ጋዜጠኞችን በራሱ አይን እያየ እራሱንና የሚወዳቸውን ሰዎች የሚያወድስበትን የድሮ አለቆቹን የሚሰድብበት ክፍል ነው፤ ይሄ ጽሁፍ ከበአሉ አሟሟት ጋር ምንም አይነት ቀጥተኛ ግንኙነት አልነበረውም። በአሉ በወቅቱ በስራው ደስተኛ አልነበረም። ከስራ ባልደረቦቹ ጋርም ጥሩ ግንኙነት አልነበረውም ይለናል። አበራና በአሉ አንድም ቀን ተገናኝተው ሻይ ጠጥተው እንደሚያውቁ አልነገረንም። በአሉም በስራዬ ችግር አለብኝ ብሎ ለአበራ አልነገረውም፤ የተገናኙት ከ2 ጊዜ አይበልጥም፤ እሱንም በአሉ የስራ መመሪያ ሊሰጠው ቢሮ ጠርቶት፤
በዚህ በመጨረሻው የአበራ የፕሮፖጋንዳ ጽሁፍ ውስጥ ውና የጥቃት ሰለባ የነበሩት ጋዜጠኛ ገዳሙ አብርሃ ናቸው። ብዙ በሙያው የለፋና ሰውዬውን የሚያውቁ ሰዎች እንደሚሉት የኢትዮጵያ ታሪክ በትክክለኛ ሰዎች ሲፃፍ ገዳሙ አብርሃ በጋዜጠኛነት ሙያ አንቱ ከተባሉት ተርታ ይመደባሉ። ወዳጄ አለማየሁ እንደሚለው ጋዜጠኛነት እንደወታደር ማእረግ ቢኖረው ባለ 4 ኮከብ ጄኔራል የሚባል ስልጣን ሊሰጣቸው የሚገባ በኢትዮጵያ ጋዜጠኛነት ሙያ ከፍተኛ አስተዋፆኦ ያደረጉ ያገር ባለውለታ እንደነበሩ ከታሪካቸው፣ ከሰሩት ስራ በቀላሉ ማወቅ ይቻላል።

ገዳሙ ዛሬ በህይወት የሉም። አሁን አበራ ስለሚከሳቸው ክስ ከመቃብር ተነስተው መልስ አይሰጡትም። ለነገሩ በህይወት ቢኖሩም መልስ የሚሰጡት አይመስለኝም። አበራ ገዳሙን የለየላቸው ሻእቢያ ናቸው ይለናል፤ ገዳሙ ፀረ አንድነት አቋም ስለነበራቸው ሌሎች ኢትዮፕያዊ ጋዜጠኞችን ያሰቃዩ ነበር፣ ገዳሙ በበአሉ ስልጣን የሚቀኑ ሰው ነበሩ፣ ይለናል። እውነታው ግን ገዳሙ ጥርት ያሉ ኢትዮጵያዊ እንኳን ኤርትራን ከሚያስገነጥለው ሻእቢያ ይቅርና ከየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት ጋር ምንም አይነት ንክኪ የሌላቸው ነፃ ጋዜጠኛ ገዳሙ ጋዜጠኛነትና ፖለቲካ ተለያይተው መታየት አለባቸው የሚል ትክክለኛ የጋዜጠኛነት አቋም ላይ የተመሰረቱ፣ በሌሎች ጋዜጠኞችም እንደ ሞዴል የሚታዩ ነበሩ።

አበራ የገዳሙን ስም ለማጥፋት ለምን ፈለገ? ብለን ከጠየቅን መልሱ አንድና አንድ ነው፤ በራሱ በአበራ ጽሁፍ ውስጥ በተለያየ ቦታ ይታያል ገጽ 10 ላይ “ገዳሙ አብርሃ የዚህን ጽሁፍ አቅራቢና የጐበዞቹን አገር ወዳድ ባልደረቦቹን ፎቶግራፍ በማስለጠፍ ወደ ኢትዮጵያ ራዲዮ ግቢ እንዳንገባ ያከናወኑት ህገወጥ ተግባር” እነዚህ ጋዜጠኞች በገዳሙ ትእዛዝ ከስራ እንደተባረሩ ሁላችንም እንስማማለን፤ ለምን ተባረሩ ለሚለው መልስ ግን ይለያየናል፤ አበራ እንደሚለው እነአበራ የተባረሩት አገር ወዳድ ስለሆኑ፣ ገዳሙ ደግሞ ሻእቢያ ስለሆኑ ነው፣ ገዳሙን የሚያውቁ ሰዎች የሚሉት ደግሞ ገዳሙ እነዚህን ሰዎች ያባረረው መኢሶን የሚባል በወቅቱ ከደርግ ጋር ይሰራ የነበረ ድርጅት አባል ነበሩ፣ የድርጅታቸውም አባል የአራት ኪሎ ወጣቶችን የጨረሰው ግርማ የሱ ተራ ደርሶ ደርግ ሲገድለው አንደኛው የነአበራ ጓድ የግርም፣አን መሞት በዜና አልናገርም አለ በዚያ ምክንያት ገዳሙ ስራህን ስላልሰራህ ብለው ከስራ አባረሩት፤ የሱ ፓርቲ አባላት በሰውየው መባረር ሲጮሁ ጀግናው ገዳሙ ፖለቲካና ጋዜጠኛነት አብሮ አይሄድም ብለው ሁሉንም አባረሯቸው፣ አበራ ሁልጊዜ እንደሚያደርገው ይህን ታላቅ ውነት ዘለለው።

በኢትዮጵያ ፖለቲካ አንድ የተለመደ ነገር አለ፤ የአንድን ሰው ሃሳብ ሃሳቡን መቃወም ሲያቅትህ ሰውዬውን ሌላ ሳጥን ውስጥ ማስገባት፣ ገዳሙ የወሰዱትን እርምጃ ማስተባበል ስላልተቻለ ወይም የሰውዬውን ችሎታና ስራ ማጣጣል ሳይቻል ሲቀር ከሰውዬው ሃሳብ ይልቅ የሰውዬውን ማንነት መምታት ነው። በነገራችን ላይ በሃ/ስላሴና በደርግ ዘመን በኢትዮጵያ 24% የመንግስት ሰራተኛና የዩኒቨርሲቲ ተማሪ የኤርትራ ተወላጆች ነበሩ። ጥቂቶቹ ኢትዮጵያዊ ናቸው ብለን ስናስብ እነሱ ኤርትራዊ ሆነው ቢያሳዝኑንም ብዙዎቹ የኤርትራ ተወላጆች ከማንም የበለጠ ኢትዮጵያዊነት የሚሰማቸው በኢትዮፕያ ብዙ የሰሩና ዋግ አየከፈሉ ናቸው። አልበርት አንሰታይን በአንድ ወቅት እንዲህ አለ፤ ጥሩ ከሰራሁ አሜሪካኖቹ አሜሪካዊ ነው ይሉኛል፣ እነሱ የማይፈለጉትን ካደርጁ አሜሪካኖቹ ጀርመናዊ ነው ይሉኛል፣ ጀርመኖቹ አይሁድ ነው ይሉኛል..እንደሚለው ታላቁን የኢትዮጵያ ጋዜጠኛ ገዳሙን ሻእቢያ ማለት ትክክል አይደለም።

አበራ ለማ በጅብ የጀመሩትን ታሪክ እኔ በውሻ ልጨርሰው፤ ጀግናው አሉላ አባነጋ በዶጋሊ ጦርነት ወራሪውን ጠላት ድል በማድረግና 500 የጣሊያን ወታደሮች በመግደላቸው ብዙ ጣሊያኖች ተናደው እንደነበረ ይታወቃል። ከነዛ መሀል አንዱ በጣም የተናደደ ጣሊያን ውሻውን አሉላ ብሎ ጠራት፤ ውሻ ከለታት አንድ ቀን ኢትዮጵያዊው የጣሊያን አሽከር ውሻዋን ጫካ ወስዶ ገደላት፣ ጣሊያኑ ውሻዋን ሲጠራት አትመጣም፤ ጣሊያኑ አሽከሩን ጠርቶ ውሻዋ የት ደረሰች?. ብሎ ሲጠይቀው ስሟ ከብዷት ሞተች አለው ይባላል።
እኔም የአበራ ለማ ፅሁፍ ድንቅ መባሉ አበራ በጽሁፉ ዋና ምንጭ የተጠቀመባት ገነት አየለ “መርማሪ ፀሐፊ” መባሏ፣ ለዚህ ሁሉ አላስፈላጊ ውዝግብ ምክንያት የሆነው የነገነት አየለ የፈጠራ ሰው ጓድ ቁጥር 53 “ቱባ የደርግ ባለስልጣን ” መባሉ ከሁሉ ደግሞ ራሱ አበራ ለማ ጋዜጠኛ መባሉ እንደውሻዋ የተሸከሙት ስም እንደከበዳቸው አሳይቶኛል።

↧

ተስፋዬ ገብረአብ ይናገራል (ቪድዮ)

$
0
0

ተስፋዬ ገብረአብ በኦሳ ጋባዥነት እዚህ አሜሪካ ይገኛል። ሰሞኑን ያደረገውን ንግግር ለግንዛቤዎ ቪድዮ ተመልከቱት።

ተስፋዬ ገብረአብ ይናገራል (ቪድዮ)

↧

An act of Boycott (እቀባ የማድረግ ርምጃ) በአሸባሪነት ያስቀጣ ይሆን?

$
0
0

ጌታቸው ፏፏቴ

Boycottየ21ኛው ክፍለ ዘመን ፋሽስቶች የኢትዮጵያን ሕዝብ በኃይል አንበርክኮ ለመግዛት የመንግሥትን የሥልጣን ቦታ ከያዙ አንድ መቶ ሺ ስምንት መቶ ቀኖች(100800) ሆነዋል።በእነዚህ ቀኖች ውስጥ ታዲያ በእያንዳንዷ መንደር አንድ ሰው ይገደላል፤አንድ ሰው ይታሰራል፤አንድ ሰው ታፍኖ ደብዛው ይጠፋል፤የብዙ ሰዎች ሀብት ይዘረፋል፤ ብዙ ሰዎች ኮቴ ኮቴያቸውን እየተቀጠቀጡ አገር ጥለው እንዲወጡ ይደረጋል፤ብዙ ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ይደበደባሉ፤ብዙ ሰዎች አካለ ጎደሎ እንዲሆኑ ይደረጋል፤ብዙ ሰዎች በርሃብ ይቀጣሉ፤ብዙ ሰዎች ህክምና እንዳያገኙ ይከለከላሉ፤የብዙ ሰዎች ጉዳይ ፍትህ ሳያገኝ ያድራል፤በሕግ ዓምላክ የሚባልበት ቦታ ሳይኖር ነው እነዚህ ቀኖች የነጐዱት።

ይህን እኩይ ድርጊት የሚፈጽመው ደግሞ የኢትዮጵያ አንድነትና ነፃነት ታሪክ አልዋጥህ ያላቸው፤ካንዴም ሁለት ጊዜ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስደፈር ሞክረው አልሳካ ያላቸው የምእራቡ አለምና የመካከለኛው ምሥራቅ ዐረብ ቱጃሮች ቅጥረኛ የነበሩ የባንዳ ልጆች ስብስብ ነው።የዚህ መረጃ ወይም ይህን ጉዳይ ጭብጥ ለማድረግ ሩቅ መሄድ የሚያስፈልገው አይደለም።ታሪክን አገላብጦ ማንበብ ነው።ዛሬም ቢሆን ይህን እኩይ በጥላቻ የበቀለና ያደገ ቅጥረኛ ድርጅት እንደ ተሰባሪ ዕቃ ተንከባክበው የያዙትና ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርጉት እነዚህ የኢትዮጵያ ጠላት አገሮች ናቸው።ይህን የመሰለ ድጋፍ ባይቸርለት ኖሮ ህወሃት በኢትዮጵያ ምድር አንድ ቀን እንኳን ማደር ባልቻለ ነበር።

መሬት በሰው ልጅ ሙት አካል ስትጫንና የንጹሓን ደም እንደ ውሃ ሲጎርፍ ከዚህ በፊት በኢትዮ-ሶማሌ፤በኢትዮ-ኤርትራ፤በሱዳን መሐዲስቶች፤በግብጽ፤እንግሊዝ፤ቱርክ፤ጣሊያን እንዲሁም እንደ ህወሃት አገር በቀል የሆኑ የግራኝ መሀመድና ዮዩዲት ጉዲት ወረራ ሲካሄድ መከሰቱን ከታሪክ የተማርነውና በአይናችንም ያየነው እውነታ ነው።የቅርብ ጊዜውን የደርግን አረመኔያዊ ጭፍጨፋ ስናነሳም ጥቃቱ የተሰነዘረውና ኢላማው ያደረገው አቅም የሌለውንና ያልተደራጀውን ድኻ አርሶ አደርና ሰርቶ የሚበላ ከተሜ ነበር።

እነዚህን ዘመናዊ ፋሽስቶች የተለየ የሚያደርጋቸው “የምንፈልገው የኢትዮጵያን ህዝብ ሳይሆን  ያፈራውን ሀብትና መሬቱን ብቻ ነው”ብለው የተነሱና በሰው ልጅ ላይ በሚደርስ አሰቃቂ ድርጊት የሚደሰቱ መሆን ነው።መሬቱን ሸጠዋል፤ለተባባሪ የጎረቤት አገሮች በነፃ ሰጥተዋል፤የሀገርና የሕዝብ ንብረት ዘርፈዋል፤ትውልደ ኢትዮጵያውያንንም እንደ ጎመን እየመተሩ ቀጥለዋል።ጊዜው ደርሷል መሰለኝ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ጭራሹን እንደ አበደ ውሻ ያክለፈልፋቸው ጀምሯል።አንድ አበአዊ አነጋገር አለ »ካልጠገቡ አይዘሉ ካልዘለሉ አይሰበሩ«እንዲሉ ጠገቡ ዝላይም አበዙ የቀረው መሰበርና መሰባበር ነው።ይህን ሁሉ ያመጣው የህዝብና የሀገር ሀብት ተዘርፎ፤ በሀገር ስም የሚለመን የውጭ እርዳታና ከበጎ ለጋሽ አገሮች የሚሰጥ ድጎማ ወደ ህወሃት ካዝና በመግባቱ ነው።

የተተኪውን ትውልድ ተስፋ የሚያጨልም ሴራም እየተካሄደ ነው።የፊተኞቹ ገዥዎቻችን ያሸከሙን የውጭ ብድር ወገብ አጉብጦ እያለ የዛሬዎቹ አይቶ አያውቁ ብሔራዊ ሞራል የሌላቸው ማህይማን ስብስቦች ደግሞ ብድርንና እርዳታን መደበኛ ተግባራቸው በማድረግ ቀጣዩ ትውልድ ከፍሎ የማይዘልቀው እዳ እየከመሩለት ነው።በብድርም ይምጣ እርዳታ መልክ ለሀገር ልማትና ለውስጥ ጉዳይ ውሎ ቢሆን እሰየው ለቁምነገር ውሏል ይባል ነበር።ይህ ግን ገንዘቡ ከመጣበት አገር ተመልሶ በግለሰቦች አካውንት ገብቶ ወደ ግል ሀብትነት መቀየሩ ነው ጉዳዩን የተለየ የሚያደርገው።

አንዳቸውም ሥራቸው አልቆ ለሕዝብ አገልግሎት መስጠት ጀመሩ የሚል ዜና ሰምቸ ባላውቅም ህዝቡን ለማደናገርና ወደ መብት ጥያቄ እንዳይሄድ ለማድረግ በርካታ ፕሮጀክቶች መወጠናቸውን ግን እሰማለሁ። በኢትዮጵያ ስም ከውጭ የሚገኘው ድጎማ ብቻውን የአባይን ግድብ ማስጨረስ ይችላል። ወይም በቅርቡ እንደሰማነው 488 የመንግሥት ቤቶች ለ23 ዓመታት ያህል አንዲት ቀይ ሳንቲም ገቢ ሳያስገኙ የትግራይ ወንበዴዎች በነፃ የኖሩበት ሂሳብ ቢወራረድ የስኳሩንም የአባይንም ጉዳይ ማስፈፀም በቻለ ነበር። ዳሩ ግን ሁኔታው ሌላ ነው ሕዝብን እያዘናጉና እያጭበረበሩ ለመኖር በሌላ መንገድ ደግሞ ኢትዮጵያዊነትን ማጥፋት ነው ማጠንጠኛው።

በነገራችን ላይ አዲሱ ለገሰ አንድ ወቅት በድሬ-ቱቢ ሲናገር ከወንድሙ ጋር በመሆን አባቱን ትጥቅ አስፈታነው ሲል ሰምታችሁ ከሆነ አባቱን ማዋረዱ ሳይሆን የታየው ሀቀኛ አብዮታዊ መሆኑን ነው።እኔ ስከማውቀው ድረስ ደግሞ አዲሱ ወላዋይና አድር ባይ አስመሳይም ነው።የ488 የመንግሥት ቤቶች የወንበዴዎች መኖሪያ መሆኑን ካጋለጡት መሀል አንዷ እንወይ ገብረመድኅን ስትሆን እንዲህ እንደ ዛሬው ብርጫው ሰፊ ባልነበረበት ወቅት እንወይ የአዲሱ ለገሰ ሚስት ነው የነበረች።ታዲያ ጀግናችን አዲሱ ለገሰ የጋሊቲ ሰፈር ልጅ እንወይን ከሥራ አስባረረ፤በዱላም አስደበደበ ታዲያ ይህ ሰው ነው ወይስ አውሬ?እንወይ ለአዲሱ በጣም የምትልቅበት እንጅ የምታንሰው አይደለችም።አዲሱ አሁን ደግሞ ህወሃት የግንባሩን አባላት ገለል በሉ ብሎ ብቻውን መሰብሰብ ሲጀምርና ሌሎችን ከጨዋታ ውጭ ሲያደርግ የአዲሱ ለገሰ ምርጫ ምን ሊሆን ይችል ይሆን?

ወደተነሳሁበት ሳልገባ ብዙ ነገር ነካካሁ እንደምናውቀው ማንኛውም መንግሥት ሲሄድ ሌላ መንግሥት ይተካል።በዚህ ሰአት አዲሱ መንግሥት በመንግሥት ይዞታ ሥር የነበሩ የመንግሥት የተባሉ ተቋማትን ፤ገንዘብን፤ሌሎች የጦር ኃይልን ፤የአየር መንገድን፤የትራንስፖርት አገልግሎትን፤ሕንፃዎችን ከሂያጁ መንግሥት ይረከባል ወይም በኢትዮጵያችን እንደተለመደው በኃይል ይወርሳል።የአሁኑ ሁኔታ ግን በጣም የረቀቀና በአይነቱ የተለየ ነው የጭነትም ሆነ የሕዝብ ማመላለሻ አገልግሎት ሰጭ ተቀሟት፤ራሱ አየር መንገድና የጦርና የፖሊስ ኃይልን ስንመለከት በአንድ ጎሳ የሚመሩና የህወሃት አገልግሎ ሰጭ ናቸው።ጉኡዝ የሆነውን ሕንፃም ይዘውት ባይሄዱም የመጨረሻዋ ቀን ስትደርስ እንደሚያፈርሱት ይታወቃል።

አንድ በወር 4.000.00 ዶላር ገቢ ሊያስገኝ የሚችልን ሕንፃ አንድ የህወሃት አባል የሆነ ሰው ለ23 ዓመታት አንዲት ቀይ ሳንቲም ሳይከፍል መኖር ሲባል በ488 ሕንፃዎች ኢትዮጵያ ልታገኝ ይገባት የነበረውን ገቢ ማሳጣት ማለት እንደ-እኔ ድምጹ በማይሰማ መሣሪያ ኢትዮጵያን መግደል ነው።ይህ አሀዝ ለጊዜው ይቅርብ እንጅ የእነዚህ እኩያን ተግባር ወደ መሀል ገባ ብሎ ሲታይማ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን ዓለምን የሚያስደምም ነው የሚሆነው።

«በሬ በስድብ አይታረስም»እንዲሉ ህወሃትን በሰላማዊ ሰልፍ፤በስድብና በጥላቻ ብቻ እንደማንጥለው አውቀን ጥጋቡ ከልኩ አልፎ ዝላይ ስለጀመረ ዘሎ እንዲሰባበር ማድረግ የኛ ፋንታ ነው።በብድር በልገሳ ከውጭ የሚገኝ ገንዘብና ቁሳቁስ፤በሀገር ውስጥ የመንግሥት የነበረና ከሕዝብም የተዘረፈ ገንዘብና ሀብት በህወሃት እጅ ገብቶ ስለሚገኝ ሕዝብ በዚህ ላይ ዘመቻውን ማጧጧፍ ይገባዋል።ዘመቻው ግን የተደራጀና መሪ ያለው መሆን አለበት።መሪ የሌለው ዘመቻ ውጤቱ መጥፎ ሁኔታዎችን ሊያስከትል ስለሚችል የተቃዋሚ ኃይሎች ኃላፊነቱን መውሰድ አለባቸው።በቅርቡ ድምጻችን ይሰማ በማለት ህወሃትን እያርበደበዱት የሚገኙት እስላም ወገኖቻችን ያደረጉትን የ24 ሰአት የቴሌፎን አለመደወል እቀባ እንደ አንድ አብነት ወስደን በሚከተሉት የህወሃት ተቋማት ላይ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ እቀባ ማድረግ ከቻልን የህወሃት ጥጋብ በመጠኑም ቢሆን ሊተነፍስ ይችላል ብየ አስባለሁ።

1/ገንዘብ መላክ፦አብዛኛው ኢትዮጵያዊ አነሰም በዛ የሰውነቱ ክፋይ ለሆኑ ወገኖቹ ወደ ሀገር ቤት ገንዘብ ይልካል ይህ የሚላከው ገንዘብ ደግሞ የህወሃት ወደ ሆነው ባንክ ሄዶ ይገባል በዚህ ምክንያት የህወሃትን የገንዘብ(የዶላር) እጥረት ቀረፍንለት ማለት ነው።በሌላ መንገድ ሳናስበው ህወሃትን እያጠናከርን እንደሆነና ሀገር ከሚያፈርስና ህዝብ ከሚጨፈጭፍ ፀረ-ሕዝብ ድርጅት ጋር ተባብረናል ማለት ነው የሚሆነው።ስለዚህ የህወሃትን ባንኮች ለይቶ ማወቅና በነዚህ ባንኮች ገንዘብ አለመላክና አለማስቀመጥ አንዱ ይሆናል።

2/ድሮ የመንግሥት የነበሩ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ሥራ እንዲቆም በማድረግ ቦታውን ህወሃት ተክቶ እየሠራበት ይገኛል።የሌሎች የግል ባለሀብቶችን የትራንስፖርት አገልግሎት መጠቀም መቻልና ህወሃትን ከመተባበር መቆጠብ።

3/አቅሙ የተመናመነ ቢሆንም በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ህወሃት ገቢ በሚያገኝባቸው ተቋማት ለምሳሌ እንደ ዳሽን ቢራ የመሳሰሉትን ህዝቡ ይገለገልባቸዋል ይህ ደግሞ በተዛዋሪ የፀረ-ሕዝብ ካምፕን ማጠናከር ነው የሚሆነው ስለዚህ በዚህ ዙሪያ ርምጃ(አቋም) መውሰድ ያስፈልጋል።

4/ሆቴሎች፤ሬስቱራንቶች፤ቡና ቤቶች፤ምግብ ቤቶች፤ግሮሰሪዎች በህወሃት እጅ እንደወደቁ ይታወቃል እነዚህን በሀገር ቤትም ሆነ በውጭ አገር ህዝቡ ዘር እንዳይልባቸው ቢደረግና የሌሎችን አገልግሎት ሰጭ ድርጅቶችን ምርት ብንጠቀም ወገንን እረዳን እኛንም ጠቀምን ማለት ነው አልጠግብ ባዮችንና ስግብግቦችን ደግሞ ትምህርት እንዲሆናቸው አደረግን ማለት ነው።

5/በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ትብብርን መንፈግ፤ደህንነት፤ፖሊስና የአጋዚ ሠራዊት አባላትን ስምና የኃላፊነት ደረጃ ማወቅ፤የሚሠሩትን ዘግናኝ ተግባር ዘግቦ በፌስ ቡክና በሌሎች ድረ-ገጾች እንዲነበብ ማድረግ፤አንድ ግለሰብ ላይ ጥቃት ሲሰነዘር ሌሎቻችን ጩኸት ማሰማትና ማደናገጥ ላልሰማው ማሰማት…ወዘተ ተግባራት ገቢራዊ ለማድረግ የተቃዋሚ ኃይሎች የሚከተሉት መንገድ ሊሆን ይገባል ብየ አምናለሁ።

በመጨረሻም ከአንዳርጋቸውና ከሌሎችም እንደተመለከትነው የውጭ አገር ዜግነት አለኝ ብሎ መዘናጋት ከንቱነት ነው።ለአሜሪካም ሆነ እንግሊዝና ሌሎች አገሮች የሚቀርበው አቤቱታና ሰላማዊ ሰልፍም ለጊዜው ስሜትን ለማብረድ ካልሆነ የሚገኝበት ተስፋ የለም።አቀናባሪውና ከኋላ ሆኖ አይዞህ ባዩ ማን ሆነና? ይልቁንስ አንድ ሕዝቡም ሆነ የተቃዋሚ ኃይሎች እጅግ ጠቃሚ መሆኑን እያወቅን ነገር ግን በተግባር የማንፈጽመው ጉዳይ «ህወሃት አጥብቆ የሚፈራውንና የሚጠላውን አንድነት መፍጠር አለመቻል ነው»ይህ ደግሞ ኃላፊነት የጎደለው በሀገርና በህዝብ ላይ ያለንን ደካማ አስተሳሰብ አጉልቶ የሚያሳይ ነው።አመንም አላመን ህወሃት በሚሄድበት መንገድ እየሄድን እንደሆነ ልንቀበለው ይገባል።አሁን በቅርቡ ብቻ ህወሃት የግንባሩ አባላትን እያገለለ የሚሄድበትን መንገድ እንኳ ተገንዝቦ መቀስቀሻ ነጥብ አለማድረግ ትልቅ ድክመት ነው ብየ አምናለሁ።

ቸር ይግጠመን፦ ጌታቸው ፏፏቴ

↧
↧

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ከ1986-2006 ዓ/ም (ሚሊዬን ዘ አማኑኤል) »

$
0
0

dd

ከሚሊዬን ዘ አማኑኤል

በመንግስት ልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ባለፈው 20 አመታት 365 መንግስታዊ ድርጅቶች ወደ ግል ዘርፍ ተዛውረዋል!!!  እስከ 1986 ዓም ድረስ ወደግል ከተዛወሩ የልማት ድርጅቶች 3.3
ቢሊዩን ብር ተገኝቶል:: ከ1997 ዓ/ም እስከ 2006 ዓ/ም ድረስ ደግሞ 15 ቢሊዩን ብር ተገኝቶል፡፡ በድምሩ 18.3 ቢሊዩን ብር መገኘቱን የተሰበሰበው ገቢ ግን 4 ቢሊዩን ብር ብቻ መሆኑን
እስረድተዋል፡፡  [ሙሉውንለማንበብእዚህላይይጫኑ]

↧

የኢፈርትና ሜድሮክ የቢዝነስ (ሞኖፖሊ) ምፓየር በኢትዬጵያ (ሚሊዩን ዘ አማኑኤል)

$
0
0

ddከሚሊዩን ዘ አማኑኤል የኢትዬጵያ ኢኮኖሚ በሁለት ትልልቅ የቢዝነስ ሞኖፖሊዎች ቁጥጥር ስር ይገኛል፡፡ Aንደኛው በህወሃት የፖለቲካ ድርጅት የሃብት ቁጥጥር ስር የሚገኘው በስጦታ የተላለፈ ሃብት ለትግራይ መልሶ ማቆቆም The Endowment Fund For The Rehabilitation of Tigrai (EFFORT) የሚባል ሲሆን የዚህም የሃብት ምንጭ ህወሃት በሽፍትነት ለአስራ ሰባት ዓመታት ከኢትዬጵያ ህዝብ የዘረፈው ሃብት ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ (ሜድሮክ) ሞሃመድ ዓለም ዓቀፍ የእድገትና ጥናት ድርጅት ካንፓኒዎች Mohamed International Development Research Organization  Companies (MIDROC) —– [ሙሉውንለማንበብእዚህላይይጫኑ]—    

↧

የሚዲያ አፈና ትግሉን ያጠናክረወል እንጂ አያቀጭጨውም ! (ከይድነቃቸው ከበደ)

$
0
0
(ይድነቃቸው)

(ይድነቃቸው)

ተሰባስቦ መቃወም እንዲሁም መደገፍ፣ አንድ ሰው የሚመስለውን ሃሳብ በፈለገው መንገድ መግለፅ፣ የመምረጥና የመመረጥ፣ መንግስትን የመተቸት፣ በራስ ፍቃድ የመናገረ እና ያለመናገር ፣ በዓልንና አይማኖትን መከተልና ማስፋፋት እንዲሁም ህግ ለሁሉም የሚሰራስ ለመሆኑ መረጋገጥ እና የመሳሰሉት ሁሉ ተግባራዊ የሚሆነው ተአቅቦ ያልተደረገበት የመናገርና የመረጃ መብት ልውውጥ ተግባሪዊ ሲሆን ብቻ ነው፡፡ ሰው በመናገሩ አና በመፃፉ ብቻ ለእስር እና ለስደት የሚዳረግበት አገር በዋነኝነት ከሚጠቀሱት ውስጥ ኢትዮጵያ አንዶናት፡፡ ነገር ግን ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት የአመለካከት እና ሐሳብን በነፃ የመያዝና በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ የመግለፅ ነፃነት አለው፡፡የሚለው በኢትዮጵያ ህገመንግስቱ አንቀፅ 29 ተፅፎይገኛል፡፡ በእርግጥ ይህ መብት ገደብ ሊጣልበት እንደሚችል በህገመንግስቱ ላይ ተገልፆ የተቀመጠ ሲሆን ገደብ ግን መሠረታዊ የሆነውን መረጃን የመስጠት እና የማግኘት እንዲሁም አስተሳሰብላይ ወይም አመለካከት ላይ ውጤት እንደማይኖረው በህገመንግስቱ ተገልፆይገኛል፡፡
ይሁንእንጂ አሳብን በነፃ ማሰብና ማንሸራሸር በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ እጅግ አዳጋች ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ አልፎ ተርፎ በአስተሳሰብ ወይም በአመለካከት ላይ ተፅኖ እስከመፍጠር ተደርሶኦል ፡፡ ነገር ግን እንዲህ አይነቱ ሁኔታ ለህግም ሆነ ለሞራል ተቃራኒ እንደመሆኑ መጠን የፈጀውን ፈጅቶ ወደ ነበረበት መመለሱ የማይቀር ሃቅ ነው፡፡በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለህዝቡ ተገቢውን መረጃ እያስተላለፉ ያሉ የእትመት ውጤቶችን ከገቢያ ለማውጣትና ፈርጆ ለመክሰስ እየተደረገ ያለው ዝግጅት ሌላው ማሳያ ነው፡፡ ጋዜጠኞችን በማሰቃየት፣ በማሰር እና እንዲሰደዱ በማደረግ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ በሁለተኝነት ደረጃ ላይ ትገኛለች ፡፡ መንግስትን ተችቶ የፃፈና ፁሁፉ የወጣበት ጋዜጣ ወይም መፅሔት ጨምሮ ሁሉም ለእስር የሚዳረግበት ወይም አደገኛ ዛቻና መስጠንቀቂያ የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡
በዲሞክራሳዊ ሥርዓተ ዜጎች የሚኖሩት ግልፅ በሆነ የሃሳብ ልውውጥ ነው፡፡ የትኛውም አይነት ሃሳብ ከማንም ሊመጣ ይችላል ቁም ነገሩ መሆን ያለበት የሚመጣው ሃሳብ የሚመከተው በምንድነው የሚለው ነው፡፡ ለነፃ ንግግር ችግር የተሻለው መንገድ የበለጠ ነፃ ንግግር ነው፤ አሳብን በመግለፅ መብት ላይ የሚደረግ ማናቸውም ተፅእኖ ሲውልሲያድር በእያንዳንዱ ግለሰብ የመናገር መብት ላይ ስጋት ሊያስከትል ይችላል፡፡ ለዚህም ነው ወደነበረበት መመለሱ የማይቀር ነው ለማለት የሚያስደፍረው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ማንም ሰው በስጋት ውስጥ መኖርን ስለማይፈልግ ነው፡፡
በመሆኑም በአገራችን እየከሰመ ያለው ሃሳብን በነፃ የመግልፅ እና መረጃ የማግኘት መብት በገዥው መንግስት መልካም ፍቃድ ላይ የተመሠረት ወደመሆን ደረጃ ተሸጋግሯል፡፡ የፈለጉትን መስማት እና ማዳመጥ እንዲሁም በፈለጉት የመገናኛ ብዙሃን መንገድ ሃሳብን መግለፅ እና መረጃን ማግኘት ግለሰብ ከሆነ እንደግለሰቡ፣ ተቋም እንደተቋም እንዲሁም ፓርቲ እንደ ፓርቲ የመምረጥ የራስ መብት ነው፡፡ ይህ ደግሞ አንዱ የዲሞክራሲ መገለጫ ባህሪ ነው፡፡
ሌላው እና አሳሳቢ ሊሆን የሚገባው ሰው የመረጠውን መስማትና ማዳመጥ እንዲሁም ማንበብ መብቱ እንደጠጠበቀ ሆኖ ግለሰብ ወይም ተቋም ሃሳቡን እንዴት የመግለፅ መብት እና ግዴታ አለበት የሚለው ነው፡፡ ይህን በተመለከተ ተቋም ወይም ግለሰብ ሃሳብን ወይም መረጃን በማንኛውም መንገድ የመገልፅ ሙሉ መበት በህግ የተጠበቀ ነው ፡፡ እንዲኹም የዚህ መብት ተቃራኒ የሆኑ ማናቸውም ነገሮች ተቀባይነት እንደሌላቸው በህገመንግስቱ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በዚህም መሰረት በማናቸውም የመገናኛ ብዙሃንሃ ሳብን መግለፅ እና መረጃን መስጠጥ በራሱ ወንጀል ወይም ጥፋት አይደለም ይህ የሆነው ደግሞ መብት ከመሆኑ አንፃር ነው፡፡ በመሆኑም በኢዲስ ጉዳይ፣ ፋክት፣ ሎሚ፣ .እንቁ እና ጃኖ መፅሔት ላይ መንግሰት ክስ የመሠረተበት ዋንኛ ምክንያት ሃሳብን የመገለፅ እና የሚዲያ ነፃነት በማፈን የለየለት አምባገነናዊ ስርዓት በአገራችን በማስፈን ስልጣንን ለማረዘም የተደረገ መፍጨርጨር ነው፡፡ የህዝብ የስልጣን ባለቤትነት ለማረጋገጥ እና ለዲሞክራሲ ማበብ የሚደረገው ጥረት በይበልጥ እጅ ለእጅ ተያይዘን እስከድል ጫፍ የምንደርስበት እንጂ ወደኋላ የማንል መሆኑ ወያኔ ጠንቅቆ ሊያውቅ ይገባል፡፡
ይድነቃቸው ከበደ
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!

↧

የሳዑዲ ዓረቢያ ንጉስ አብዱላህና ሽህ ሞሃመድ አላ አሙዲ (ከሚሊዬን ዘ አማኑኤል)

$
0
0

ddከሚሊዬን ዘ አማኑኤል የሳዑዲ ዓረቢያ ንጉስ አብዱላህ አነሳሽነት የተጀመረው የሳውዲ የግብርና ዘርፍ መርሃ ግብር መሬት በሚሸጡ ደሃ አገራቶች መንግስታት ላይ በማተኮር፤ በባህር ማዶ አገራት የሚገኙትን ለም መሬቶች በሳዑዲ መንግስት ስም በሸያጭና ወለድዑግድ የመሬት ይዞታ/ንብረትን በግዥ’ በኮንትራት ‘በሊዝ ባለቤትነት በመያዝ Aስፈላጊውን የመዋኢለ ንዋይ ፍሰት/ ኢንቨስትመንት/ በማድረግ የግብርናውን ምርት ወደ ሳዑዲ በመላክ ህዝቡን መመገብ የሚል ነው፡፡ —--[ሙሉውንለማንበብእዚህላይይጫኑ]—–  

↧
↧

በመንግስት ሞኖፖሊ የተያዘው የኢትዩጵያ የባንክ አገልግሎት ዘርፍና የኢትዩጵያ ብር የገንዘብ የመግዛት አቅም ቅነሳ (devaluation) ክፍል አንድ – (ከሚሊዬን ዘ አማኑኤል)

$
0
0

ከሚሊዩን ዘ አማኑኤል

 

dd Banking sector and currency devaluation in Ethiopia በ1967 ዓም የIትዬጵያ ወታደራዊ መንግስት (ደርግ) በአዋጅ በሃገሪቱ ውስጥ የሚገኙ በግል ዘርፍየሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን በአዋጅ ቁጥር 20/1974 ወደ መንግስት ሃብትነት በማዘዋወርና በመውረስ ፋብ ሪካዎች፣ባንኮችና ኢንሹራንሰ ኩባንያዋችን፣የከተማ ትርፍ ቤቶችን፣ የገጠር መሬትን፣ ኢርሻዎችን ወዘተ በመንግስት ተወረሱ፡፡  የኢትዬጵያ ወታደራዊ መንግስት (ደርግ) አፍቃሪ ሶሻሊስት መንግሥት የፖለቲካና ኢኮኖሚ ፖሊሲዎች በማማከርና በማርቀቅ አገሪቷን ወደ ሶሻሊስት የእቅድ ኢኮኖሚ እንድትከተል አደረጉ፡፡–—[ሙሉውንለማንበብእዚህላይይጫኑ]—–

↧

በመንግስት ሞኖፖሊ የተያዘው የኢትዩጵያ የባንክ አገልግሎት ዘርፍና የኢትዩጵያ ብር የገንዘብ የመግዛት አቅም ቅነሳ (devaluation) ክፍል ሁለት (ከሚሊዬን ዘ አማኑኤል)

$
0
0

dd4ኛ) የኢትዩጵያ ብሄራዊ ባንክ በባንክ አገልግሎት ዘርፍ የህዝቡን ታማኝነት ኢንዲያገኝና የፋይናንስ ዘርፉን ኢንዲያስተዳድርና ኢንዲቆጣጠር ተጨማሪ መመሪያና ደንብ ማውጣት ያስፈልጋል፡፡ የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ በሃገሪቱ ውስጥ ስንት ቅርንጫፍ ባንኮች ኢንዳሉትና በክልላዊ መንግስቶች ውስጥ ያለው ስርጭት፣ማለትም የኢትዩጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ቁጥር ለሚሊዩን ህዝብ፣የአነስተኛና ጠቃቅን የብድርና ቁጠባ ኢንስቲቲውሽን (MFI) አገልግሎት ተጠቃሚ ህዝብ በመቶ፣የቁጠባና ብድር ኮዖፕሬቲቨ አገልግሎት ተጠቃሚ ህዝብ በመቶ (SACCO)፣በመደበኛ የባንክ አገልግሎት የተመቻቸላቸውና ተጠቃሚ ህዝብ በመቶ ቀጥሎ ባለው ሠንጠረዥ ይታያል፡፡ —[ሙሉውንለማንበብእዚህላይይጫኑ]—–

↧

የሕወሓት ጄኔራሎች ሲታመሱ ዋሉ፤ ሁለት ከፍተና የጦር መሃንዲሶች ዱካቸው ደብረዘይት ከሚገኘው እስር ቤት ተገኝቷል

$
0
0

ምንሊክ ሳልሳዊ እንደዘገበው፦

በጥርጣሬ/ግምት ካልሆነ በቀር አስራ አራቱ መኮንኖች የት እንደገቡ አይታወቅም።
ሁለት ከፍተና የጦር መሃንዲሶች ዱካቸው ደብረዘይት ከሚገኘው እስር ቤት ተገኝቷል።

ወደ መቀሌ ከዲያስፖራው ጋር ለዘረፋ የንግድ ሽርክና ኢንቨስተሮች ለመመልመል ያመሩት ጄኔራሎች ሳይቀሩ በምን እንደመጡ በማይታወቅበት ሁኔታ አዲስ አበባ ደርሰው የመሃል አገር መኮንኖች መጥፋትን ተከትሎ ያመጣውን ውጥረት በስብሰባ ሲያሹት እና ከተለያዩ ወታደራዊ ደህንነቶች መረጃ ሲሰበስቡ እንደዋሉ ታውቋል።

ፎቶ ፋይል

ፎቶ ፋይል


በሰራዊቱ ውስጥ አለመተማመን የተፈጠረው ከምን የመነጨ ነው የሚል ጥናት በዚህ ሳምንት በተካሄደበት የመሃል አገር መከላከያ መምሪያዎች ውስጥ አጋጣሚ በተገኘ መረጃ 16 ከፍተኛ የጦር መኮንኖች የት እንደገቡ አይታወቅም ሲል ሪፖርት ያቀረበው የወታደራዊ ደህንነት ቡድን የቀረበለትን ጥቆማ ለበላይ አካላት ሪፖርት ሳያድርግ ፍተሻውን አጧጡፎት የነበረ ቢሆንም ምንም አይነት ፍንጭ ባለማግኘቱ ትላንትና የተነገረው የበላይ አካል በከፍተኛ ድንጋጤ ተውጦ የዋለ መሆኑን ለጦር ክፍሎቹ ቅርብ የሆኑ ምንጮቻችን ከመከላከያ ያደረሱን መረጃ ጠቁሟል።

ከመሃል አገር በተለያየ የጦር መምሪያ ውስጥ ተመድበው ይሰሩ የነበሩት እና የአንድ ኮርስ ምሩቅ ናቸው የተባሉት ወታደራዊ መኮንኖች ውስጥ የሕወሓት ጄኔራሎች ላይ ጥርሱን እንደነከሰ የሚነገርለት ኮሎኔል አለም የሚባለውን የተንቤን ተውላጅ ጨምሮ አስረ አንዱ ወደ ደቡብ ሱዳን ዘልቀው ገብተዋል የሚል መረጃዎች ቢኖሩም እስካሁን ማረጋገጥ እንዳልቻለ ለመከላከያ ደህንነት ቢሮ ምንጮቻችን የገለጹ ሲሆን የሶስቱ ዱካ አለመገኘቱን እና ሁለት ከፍተኛ የጦር መሃንዲሶች ከየት ታፍነው በማን ታፍነው እንደተወሰዱ ሳይታወቅ በደብረዘይት የምድር ውስጥ እስር ቤት እንደሚገኙ ተረጋግጧል።

የሕወሓት ጄኔራሎችን ያመሳቸው ጉዳይ የተንቤን ተወላጆች ሌሎች የደቡብ እና የአማራ ተወላጆች ተያይዞ መጥፋት ሲሆን እንዲሁም በጦር ሰራዊቱ ውስጥ እየላላ መጥቷል ሲሉ የደነፉበት የወታደራዊ ደህንነት ቁጥጥር መላላት ለነገው የስልጣን እድሜያቸው ከፍተኛ ስጋት እንዳጠላበታ ያሳያል ሲሉ መረጃውን የላኩልን የመከላከያ ምንጮቻችን ተናግረዋል። በሙሉ የሃገሪት እዞች ከፍተኛ ቁጥጥር እና ፍተሻ እንዲካሄድ በዛሬው ስብሰባ ጥብቅ ትእዛዝ ያስተላለፉት የሕወሓት ጄኔራሎች በደቡብ እና በምእራብ ድንበሮች አከባቢ ያሉ እንቅስቃሴዎች እንዲፈተሹ በወጪ ገቢው ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር እንዲደረግ እና የየቀኑ ሪፖርት እንዲላክ እንዲሁም በመሃል አገር ያሉ የቶር መኮንኖች በየቀኑ ለቅርብ አለቃቸው ዝርዝር የአባላት እንቅስቃሴ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ጥብቅ ትእዛዝ አውርደዋል።እንዲሁም ተጨማሪ ወታደራዊ ደህንነቶች በየእዙ እንዲመደቡ አዘዋል።

በዚህ ዙሪያ ያለውን ጉዳይ በተመለከተ የወታደራዊ ደህንነት ሪፖርቶቹን እየተከታተልን የምናቀርብ መሆኑን ቃል እንገባለን።

↧

ለጋዜጠኛ አዚዛ መሐመድና የሰማያዊ ፓርቲ አባል ወይንሸት ሞላ የተፈቀደው ዋስትና ተከለከለ

$
0
0

aziza ena weyeneshet
ከአሸናፊ ደምሴ

በአንዋር መስጊድና አካባቢው ሐምሌ 11 ቀን 2006 ዓ.ም በተፈጠረ ግጭትና ሁከት ተሳትፈዋል በሚል ፖሊስ ምርመራ እያደረገባቸው ከሚገኙ 14 ተጠርጣሪዎች መካከል ጋዜጠኛ አዚዛ መሐመድና የሰማያዊ ፓርቲ አባል ወይንሸት ሞላን ጨምሮ ለሦስት ሰዎች ፍርድ ቤት ትናንት ጠዋት ፈቅዶት የነበረው የ5 ሺህ ብር የዋስትና መብት ከሰዓት በኋላ በፖሊስ በቀረበ ይግባኝ ውድቅ ሆኖ ዋስትናው ተከለከለ።

ሜክስኮ በሚገኘው የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የፖሊስ ኮሚሽን ጉዳዮች የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ማስቻያ ችሎት የዛሬ ሳምንት የተሰጣቸውን የጊዜ ቀጠሮ ተከትሎ በችሎት ካቀረቡት 14 ተጠርጣሪዎች መካከል የአዲስ ጉዳይ መጽሔት ፎቶ ጋዜጠኛዋ አዚዛ መሐመድና የሰማያዊ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል የሆነችውን ወ/ት ወይንሸት ሞላን ጨምሮ አራት የፖሊስ አባላት (ማለትም አንድ ኢንስፔክተር፣ አንድ ምክትል ኢንስፔክተርና አንድ ምክትል ሳጅንና አንድ የኮንስታብል ማዕረግ ያላቸው) እና ሌሎች ስምንት ተጠርጣሪዎች በችሎች ሲያቀርብ የተቀሩት ከሁለተኛው የጊዜ ቀጠሮ በኋላ ፖሊስ ምርመራዬን ጨርሼባቸዋለሁ ሲል ማሰናበቱን ለፍርድ ቤት ማስታወቁ ይታወሳል።

አሁን ድረስ በምርመራ ላይ የሚገኙት ተጠርጣሪዎች ጠበቃ ያልቆመላቸው ሲሆን፤ በትናንት ጠዋቱ የችሎት ውሏቸውም በባለፈው የጊዜ ቀጠሮ ወቅት ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄያቸው መሠረት ፍርድ ቤቱ፤ አዚዛ መሐመድ፣ ወይንሸት ሞላ እና ኡዝታዝ መንሱር የ5 ሺህ ብር ዋስ አቅርበው እንዲሄዱ ትዕዛዝ ቢሰጥም፤ በቀደመው ችሎት ያቀረባቸውንና ምላሽ ያላቀረበባቸውን የዋስትና መቃወሚያዎች ፖሊስ ለችሎቱ አቅርቦ አስረድቷል። ይኸውም ምርመራዬን አልጨረስኩምና ዋስትና ሊፈቀድላቸው አይገባም፤ በሕክምና ላይ ያሉና ጉዳት የደረሰባቸውን የፖሊስ አባላትንም መጨረሻ ማወቅ ያስፈልጋል በሚል ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ይግባኝ መሠረት ችሎቱ ጠዋት ላይ የተፈቀደ ዋስትና በከሰዓት ላይ ውድቅ ሆኖ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ማረፊያ እንዲመለሱ ተደርጓል።

የምርመራ ተግባራቶቼን አላገባደድኩም ሲል ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮን የጠየቀው ፖሊስ በጥቁር አንበሳ እና በፖሊስ ሆስፒታል የሚገኙትንና በብጥብጡ ወቅት ጉዳት ደርሶባቸዋል የተባሉትን ሰዎች ሁኔታና ቃል ተቀብሎ ለማቅረብ ፍርድ ቤቱን በጠየቀው ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ መሠረት የ7 ቀናት የምርመራ ጊዜ የተፈቀደለት ሲሆን፤ ለመጪው ነሐሴ 7 ቀን 2006 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።

↧
↧

ከ328 ሺህ ብር በላይ አጭበርብረዋል የተባሉ የቴሌኮም ሠራተኞች ተከሰሱ

$
0
0

በአሸናፊ ደምሴ

በኢትዮ-ቴሌኮም አዲስ አበባ ቅርንጫፍና በደቡብ አዲስ አበባ የሃና ማርያም ቅርንጫፍ ሠራተኞች የነበሩ ሁለት ሰዎች ጨምሮ በአጠቃላይ አስር የሚደርሱ ተጠርጣሪዎች የፌዴራሉ ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዐቃቤ ሕግ የደንበኞችን የሞባይል ሲም ካርድ ኮዶች በመስበር ከተለያዩ ባንኮች በሀዋላ የተላከን ከ328 ሺህ ብር በላይ በተጭበረበረ መንገድ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል ሲል ክስ መስርቶባቸዋል። ትናንት ማክሰኞ ሐምሌ 29 ቀን 2006 ዓ.ም በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 18ኛ ወንጀል ችሎት ክሳቸው በተነበበላቸው 10 ተከሳሾች መካከል አራቱ ብቻ በችሎት የቀረቡ ሲሆን፤ ቀሪ ስድስቱ በመጥሪያ እንዲቀርቡ ችሎቱ ትዕዛዝ ሰጥቶባቸዋል።
birr4123111
ክሱ በችሎት ሲቀርብ የፌዴራሉ ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዐቃቤ ሕግ ክሱን ያተተው፤ ተከሳሾቹ እርስ በእርሳቸው የጥቅም ተጋሪ በመሆንና የተሰጣቸውን የሥራ ኃላፊነት ያለአግባብ በመጠቀም የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል የሚል ነው። ዐቃቤ ሕግ በክስ ዝርዝሩ፤ 1ኛ ተከሳሽ አማኑኤል አለሙና 2ኛ ተከሳሽ ዮናስ ኃይሉ በቴሌኮም ካርድ ሽያጭ መደብ ውስጥ በማገልገል ላይ ሳሉ ከሶስተኛ እስከ አስረኛ ከሚደርሱት ግብረአበሮቻቸው ጋር በመመሳጠር ከተቋሙ የሲም ካርድ ግዢን ከሚፈፅሙ ደንበኞችን “የፒን” እና “የፒዩኬ” ኮዶችን በምስጢር በመስበር በሃዋላ የሚላክላቸውን ገንዘብ ጠልፈው መልእክቱን ካደመጡ በኋላ የደንበኞቹ ግንኙነት እንዲቋረጥ በማድረግ፤ የተሳሳተ መታወቂያ በመጠቀም ከ328ሺ ብር በላይ ለግል ጥቅማቸው በማዋል የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል ይላል።

የኮሚሽኑ ዐቃቤ ሕግ በአስር ግለሰቦች ላይ ክሱን ቢመሰርትም ሁለቱን የቴሌኮም ባልደረቦች ጨምሮ ሌሎች ስድስት ተከሳሾች በችሎቱ ያልቀረቡ ሲሆን፤ በችሎት ተገኝተው ክሳቸውን ያደመጡት 3ኛ፣ 4ኛ፣ 7ኛ እና 10ኛ ተከሳሾችም ለፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጠይቀዋል። ዐቃቤ ሕግም ተከሳሾቹ በተከሰሱበት ወንጀል ጥፋተኛ የሚባሉ ከሆነ ከ10 ዓመት በላይ በሆነ እስር የሚያስቀጣቸው በመሆኑ የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ እንዲሆን ጠይቋል።

የግራ ቀኙን ክርክር ያደመጠው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 18ኛ ወንጀል ችሎትም የተጠርጣሪዎቹን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግና ያልተያዙት ተከሳሾችም እንዲቀርቡ በማዘዝ ለነሐሴ 26 ቀን 2006 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ

↧

Sport: የሱአሬዝ ነገር ዝውውሩ በአንፊልድ ቅሬታን፤ በኑ ካምፕ ግርታን ትቷል

$
0
0

ይህ ጽሁፍ በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 65 ላይ ታትሞ ወጥቷል።

በችሎታው ‹‹ሊቅ›› ተጨዋች ፈልጉ ታገኛላችሁ፡፡ በምግባሩ ‹‹እብድ›› ብትሹም አታጣም፡፡ አልፎ አልፎ እነዚህን ሁለት ገፅታዎች በአንድ ሰው ላይ ታገኛላችሁ፡፡ ሉዊስ ሱአሬዝ ‹‹ሊቅ›› እና ‹‹እብድ›› ነው፡፡ ኡሯጋያዊው ለየትኛውም ክለብ ውድ ዋጋ የሚከፍልበት ገንዘብ ነው፡፡ እንደ ሣንቲም ብታገላብጡት ሁለት መልኩን መደበቅ የማይችል ኮከብ፡፡
suarze barcelona
ሱአሬዝ ለሚጠሉት አይመችም፡፡ የሚተቹትን በሊቅነቱ ዝም ያሰኛቸዋል፡፡ ልጁ ለሚወድዱትም አይሆንም፡፡ የቀደመ ሀጢያቱን ላለመቁጠር ሲታገሉ ሌላ ይጨምራል፡፡ የሊቨርፑል ደጋፊዎች አጥቂውን እንደ አጥፊ ህፃን ችለውታል፡፡ ሲያሳፍራቸው ደጋግመው ምረውታል፡፡ ከፉልሃም ሲጫወቱ የመሀል ጣቱን አውጥቶ መሳደቡ የሀገሪቱን ጋዜጦች እና ድረገፆች በማስረጃ ፎቶግራፍ ሲያዳርስ እንዳላዩ አልፈዋል፡፡ ሳይነካ እያስመሰለ ሲወድቅ ተከራክረውለታል፡፡ ፓትሪክ ኤቭራን በዘረኝነት ተነኮሰ ተብሎ ሲቀጣም አፅናንተውታል፡፡ በካሜራዎች ፊት የቼልሲውን ብራስላቭ ኢቫኖቪች ሲነክስም አልፈረዱበትም፡፡ በመጨረሻ በዓለም ዋንጫው ጂዮርጂዮ ኪዬሊኒን ሲነክስ ዝምታን መርጠዋል፡፡ በዚህ ሁሉ ግን ደጋፊዎቹ በውስጣቸው አዝነዋል፡፡

አሁን ሱአሬዝ የለም፡፡ በክህሎቱ እያስደሰተ በጥፋቶቹ ያሸማቀቃቸው ኮከብ ወደ ባርሴሎና ሄዷል፡፡ በእርግጥ ኡራጓዊው ይዘገይ እንደሆነ እንጂ መሰናበቱ አይቀሬ መሆኑ ይታወቅ ነበርር፡ ባለፈው ክረምት በመጀመሪያ ሪያል ማድሪድ በኋላም አርሰናል የአንፊልድን በር አንኳኩተው ሲመለሱ የአጥቂው መሰንበት ቢረጋገጥም ሊቨርፑል ውዝግብ የማያጣውን ድንቅ ተጨዋች ይዞ መቆየት እንደሚቸገር ግልፅ ነበር::

ሱአሬዝ ሲጫወት እና ትኩረቱን ሁሉ ለውጤት ሲያደርግ ከፕላኔታችን ድነቅ ተጨዋቾች አንዱ ነው፡፡ ቅፅበታዊ ሩጫው፣ ልዩ የኳስ ቁጥጥር ችሎታው እና በማንኛውም ጊዜ አደጋ የሚፈጥርበት የኳስ ንክኪ ክህሎቱ ያስገርማል፡፡ ሱአሬዝ ሲፈልግ የሁለት ቡድኖችን ጨዋታ የራሱ ማድረግ የሚችል አይነት ተጨዋች ነው፡፡ ራሱ በራሱ የሚጨርሳቸው ጨዋታዎች የመኖራቸውን ያህል ለጓደኞቹ አሳምሮ የሚያቀብላቸው ኳሶችም ቡድኑን አሸናፊ ያደርጋሉ፡፡ ኳስ በእግሩ ስር ሳትሆን እንኳን በቦታ አያያዙ እና እንቅስቃሴው ባላጋራን ያሸብራል፡፡ ለጓደኞቹም የመጫወቻ ቀዳዳ ይፈጥራል፡፡
ባለፉት ሶስት ዓመታት ከግማሽ ጊዜያት በእንግሊዝ የሱአሬዝን አስገራሚ አቅም ብዙዎች አስተውለዋል፡፡ በግራ፣ ቀኝ እግሮቹ እና በተለያዩ አካላቱ ያስቆጠራቸውን ጎሎች እንዲሁም ሀትትሪኮች ተመልክተዋል፡፡ ከማይታመን ጠባብ ማዕዘን ከመረብ ያሳረፋቸውን ኳሶች አድንቀው ቪዲዮዎቹን ደጋግመው ማየት ተመኝተዋል፡፡ በአምስት ተከላካዮች መካከል የተደረደሩ ግዑዝ ፍጥረቶች አስመስሏቸው ሲያልፍ ማየት እንግዳ አይደለም፡፡ ከመሀል ሜዳ ብዙም ልዩነት ከሌለው ርቀት የመታው ኳስ እንደ ፍፁም ቅጣት ምት በረኛን አቅመ ቢስ አድርጎ ጎል ሲሆን መመልከትም አዲስ አይደለም፡፡ ሱአሬዝ እግርኳስን ብቻ ሲጫወት ደረጃው ከእነ ሊዮኔል ሜሲ እና ክርስቲያኖ ሮናልዶ ጎራ ነው፡፡

ባለፈው ክረምት ሊቨርፑል በቅጣት በርካታ ጨዋታዎችን የሚያደርገውን አጥቂውን በከፍተኛ የዝውውር ሂሳብ እንኳን ሊገላግለው አልፈቀደም፡፡ ክለቡ ላሳየው ቆራጥነት ያገኘው ክፍያ አስገራሚ ነበር፡፡ በውድድር ዘመኑ የመጀመሪያ አምስት ጨዋታዎች ያልተሰለፈው ሱአሬዝ በመጨረሻ በሊጉ 31 ጎሎች አገባ፡፡

እነዚህን ጎሎች ሲያስቆጥር የተጫዋቹ ውጤታማነት ከፍ ማለት በግልፅ ቢታይም ኡራጓዊው ከድራማዎች ነፃ አልነበረም፡፡ በተሌም በትልልቅ ግጥሚያዎች ሳነካ አስመስሎ መውደቅ ማብዛት ከባላጋራ ቡድን አልፎ የጨዋታ ዳኞችን ሁሉ ለብስጭት ይዳርግ ነበር፡፡ ይህ ድርጊቱ ብዙ ጊዜ ዋጋ አስከፍሎታል፡፡ በሀሰት ሲወድቅ ደጋግመው ያስተዋሉት ዳኞች እውነተኛ ጥፋት ሲሰራበትም ችላ ይሉት ነበር፡፡ አንዳንድ ጊዜ በጨዋታው የመጨረሻ ጊዜያት በወሳኝ ቦታ የሚፈፀሙበት ጥፋቶች ተገቢውን ውሳኔ አለማግኘታቸው ሊቨርፑልን ደጋግሞ ጎድቶታል፡፡
ሊቨርፑል ለፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮንነትም ምን ያህል ተቃርቦ እንደነበር የሚያስታውስ ሰው ኖሮ ምናልባትም የተሻለ ውጤታማ ሊሆን እና ቡድኑንም ለድል ሊያበቃ ይችል እንደነበር ይገምታል፡፡ የሱአሬዝ ጉዳት በዚህ አይገታም፡፡ ውዝግቦቹ፣ ዘረኝነት ትንኮሳው፣ ንክሻዎቹ እና ሌሎችም ድርጊቶቹ ሊርል በቅጣት የሜዳ ላይ አገልግሎትን እንዲያጣው እና የተጨዋችነት ዋጋውም ይበልጥ እንዳይጨምር ገትቶታል፡፡ በዓለም ዋንጫው ኪዬሊኒን መንከሱ ከተረጋገጠ እና ቅጣት ከተጣለበት በኋላ ጥያቄው ሱአሬዝን ማን ይፈልገዋል? የሚለውን የሚለው ነበር፡፡ በእርግጥ በአንድ የውድድር ዘመን ቢያንስ አንድ ከባድ ውዝግብ ሳይፈጥር የማይቀረውን ተጨዋች ለዚውም የተጋነነ ሂሳብ ከፍሎ የሚወስደው ይኖር ይሆን? የሚለው ጥያቄ ምክንያታዊ ነበር፡፡ የሱአሬዝን ችግር ተቋቁሞ ከችሎታው ሊጠቀም የቆረጠ የሚመስለው ባርሴሎና አጥቂውን የራሱ አድርጓል፡፡

የአንፊልድ አሻራው

በአንፊልድ ሱአሬዝን አስታውሶ ጎሎቹን መርሳት አይቻልም፡፡ ለሊቨርፑል ከ133 በላይ ነጥብ ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 82 ጎሎች ሲያገባ በጨዋታው አማካይ የጎል ሪከርድ በጣም ጥሩ የሚባል ነው፡፡ ይህ በአውሮፓ ደረጃ በጥቅል ሲታይ ብዙ ላይባል ይችላል፡፡ ነገር ግን ሱአሬዝ በንፅፅር ከፕሪሚየር ሊግ ይልቅ ጎል ለማስቆጠር ፈተናው ዝተኛ በሆነባቸው የሆላንድ ወይም የስፔን አይነት ሊጎች ምን አይነት አስደናቂ ሪከርድ እንደሚኖረው መገመት ይቻላል፡፡
suarez
በሊቨርፑል ማሊያ ለጎል አመቻችቶ ያቀበላቸው ኳሶችም 50 ደርሰውለታል፡፡ በዚህ ላይ ተጨዋቹ እንደ አንዳንድ አትቂዎች በአነስተኛ ክለቦች ላይ ብቻ የሚበረታ አይደለም፡፡ በእንግሊዝ ዋነኞቹ የሊቨርፑል ተቀናቃኞች ላይ ደጋግሞ ጎል አስቆጥሯል፡፡ በቼልሲ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ቼልሲ እና ቶተንሃም ላይ ጎሎች በማስቆጠር እና ለጎል ምክንያት በመሆን ረብሿቸዋል፡፡ የሊቨርፑል ጎረቤት ከሆነው ኤቨርተን ጋር በተደረጉ ጨዋታዎች ያሳያቸው ብቃት ከአንፊልድ ታዳሚዎች ልብ አያስወጣውም፡፡

ሊቨርልን ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ ለመመለስ ያገባቸው 31 ጎሎች እና የፈጠራቸው ዕድሎች በአውሮፓ ለራሱም የከፍተኛ ጎል አስቆጣሪነት ማዕረግ እንዲጋራ እና በእንግሊዝ የውድድር ዘመኑ ኮከብ እንዲሰኝ አብቅቶታል፡፡ እነዚህ ስኬቶቹም የብሬንዳን ሮጀርስን ቡድን ሲጠቅሙ ለእርሱም በደጋፊዎች ዘንድ ፍቅር አስገኝተውለታል፡፡

የሱአዘሬዝ ሽያጭ የሮጀርስን ቡድን ምን ያህል እንደሚያጎድል እርግጠና ሆኖ መናገር አይቻልም፡፡ ይህ ክለብ በተለያዩ ጊዜያት ምርጥ ተጨዋቾቹን እያጣ እና በተቃራኒው እየበረታ ሲሄድ የታየ ነው፡፡ ኬቪን ኪጋን ሲለቅቅ ሊቨርፑል ተሻሽሏል፡፡ ኢያን ረሽ ሲሸጥም ቡድኑ በርቷል፡፡ የፈርናንዶ ቶሬስ ስንብትም ሊቨርፑልን ወደ ፊት እንጂ ወደ ኋላ አልጎተተውም፡፡ የተጠቀሱት ተጨዋቾች ሁሉ ስለሊቨርፑል ስኬት ቁልፎች ነበሩ፡፡ ሆኖም ሲሰናበቱ በቦታቸው የተሻሉ ተጨዋቾች መጥተው ቡድኑን ይበልጥ ጠንካራ አድርገውታል፡፡ በአንፃሩ ቀዮቹ ግራይም ሱነስ፣ ዣቪ አሎንሶ እና ስቲቭ ማክማናማንን ሸጦ ተዳክሟል፡፡ ነገር ግን በሂደት እየተካቸው ተጉዞ እነርሱ በነበሩበት ወቅት ከነበረው የተሻለ ጥንካሬ ሲያሳይ ብዙዎች አይተዋል፡፡ በ1987፣ በ2001 እና 2014 የታዩት የሊቨርፑል ቡድኖች በተለየ መለኪያ የተሻሉ እና አስደሳቾች ነበሩ፡፡
በመጪው ጃንዋሪ ሱአሬዝ 28 ዓመት ይሞላዋል፡፡ ይህም ማለት ከአሁኑ ረጅም ቅጣቱ ከተመለሰ ከጥቂት ወራት በኋላ ነው፡፡ በዚህ ወቅት ተጨዋቾ በትልቅ ብቃት እንደሚጫወት መገመት ቢቻልም በከፍተኛ ደረጃ እየተጫወተ ለመቀጠል ቢበዛ ከሶስት ወይም አራት ዓመታት የበለጠ ጊዜ እንደማያኖረው እርግጥ ነው፡፡ ክለቦች ምርጥ ብቃቱን ሊያሳይ በሚችልበት ዕድሜው ላይ ተጫዋቾቻቸውን መሸጥ አይፈልጉም፡፡ ሆኖም ኮከቡ በ30 ዓመቱ ሊያወጣ የሚችለው ዋጋ በ28 ዓመቱ ከሚያስገኘው ገንዘብ በእጅጉ ያንሳል፡፡ ከዚህ አንፃር ሲታይ ሊቨርፑል ሱአሬዝን ለመሸጡ ምክንያታዊ ሊባል ይችላል፡፡

ይልቅኑ ጥያቄው ክለቡ ተጨዋቹን ሸጦ ያገኘውን ገንዘብ እንዴት ይጠቀምበታል የሚለው ነው፡፡ ሊቨርፑል እንደ ቶተንሃም ሆትስፐር ስም ያላቸውን ውድ ተጨዋቾች ገዝቶ እንዳይከስር ትንቃቄ ያሻዋል፡፡ የኋይት ሀርት ሌኑ ክለብ ጋሬት ቤልን ሸጦ ባገኘው መጠኑ ከፍ ያለ በጀት በተሰጥኦው ላቅ ያለውን ኤሪክ ላሜላ እንዲሁም ሌሎች ሶስት እና አራት ከዋክብት ቢያመጣም አልተጠቀመባቸውም፡፡

ክለቦች ተጨዋቾቻቸውን በትክክለኛው ጊዜ ወይም በተሳሳተ ወቅት ሊሸጡ እንደሚችሉ ሁሉ በሽያጭ ያገኙትን ገንዘብ በትክክለኛ ወይም በተሳሳተ ሌላ ተጨዋች ግዢ ላይ ሊያፈስሱት ይችላሉ፡፡ ትልቅ ተጨዋች ሸጦ ሌላ ትልቅ ተጨዋች ስኬት ላያረጋግጥ ዕድል አለው፡፡ ይህ ማለት ግን አንዱን ኮከብ በሌሎች ሶስት ወይም አራት መካከለኛ ደረጃ በሚሰጣቸው ተጨዋቾች መለወጥ ይሻል ማለት አይደለም፡፡

በርከት ያሉ መካከለኛ ደረጃ የሚሰጣቸው ተጨዋቾች የቡድንን ትልቀት በመጨመር በኩል ጠቃሚ እና በአሰልታኞች ተመራጭ ናቸው፡፡ ሆኖም 80 ሚሊዮን ፓውንድ የሚያወጣ አንድ ኮከብ ዋጋቸው በነፍስ ወከፍ 8 ሚሊዮን ፓውንድ ከሚተመኑ 10 ተጨዋቾች ይሻላል? ይህንን ጥያቄ ለመመለስ 8 ሚሊዮን ፓውንድ የሚገዙትን ተጨዋቾች ማንነት ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ እንደ ፊሊፕ ኩቲንሆ ያሉትንም ይጨምራሉ? ሊቨርፑል ከሱአሬዝ ሽያጭ ያገኘውን 75 ሚሊዮን ፓውንድ በጥሩ ተጨዋቾቹ ግዚ ላይ ካዋለው እና በአዲሶቹ ከዋክብት ውጤታማ ከሆነ የኡራጓዊው ስንብት ትክክለኛ ምርጫ ተደርጎ መነሳቱ አይቀርም፡፡ የሱአሬዝ ጉዳይ ጫና ውስጥ የሚያስገባው ሊቨርፑልን ብቻ አይደለም፡፡ ባርሴሎናም በቀጣይ በተያያዥ ብዙ ጥያቄዎች መመለስ ይጠበቅበታል፡፡
suarez
ለባርሴሎና ብልሀት ወይስ እብደት?

የሱአሬዝ ዝውውር የሊቨርፑልን ደጋፊዎችን አላስደሰተም፡፡ በአንፃሩ ከባርሴሎና ደጋፊዎች ፈንጠዝያ አልተጠበቀም፡፡ የካምፕኑ ታዳሚዎች ለ27 ዓመቱ አጥቂ ፊርማ 75 ሚሊዮን ፓውንድ መከፈሉ አላሳመናቸውም፡፡ በችሎታቸው ላይ ጥርጣሬ ሳይኖራቸው የባህሪዩ ተግባር በክለባቸው ገፅ ላይ የሚያመጣው ጣጣ ያሳሰባቸውም ትቂት አይደሉም፡፡

ከደጋፊዎቹ መካከል ትክክለኛው አመለካከት የትኛው ነው? ባርሴሎና ሱአሬዝን በእግርኳሱ ታሪክ ሶስተኛው ውድ ተጨዋች ማድረጉ ስህተት ነው? ተጨዋቹ በባርሴሎና ስለሚኖረው አስተዋፅኦ እና ለአጥቂዎች ለመደላደል አስቸጋሪ ነው በሚባለው ኑ ካምፕ የሚያገኘውን ቦታ እንመልከት፡፡
የብዙ ሰዎች ችግር ዝውውሮች ከገንዘብ አንፃር ብቻ ለመመዘን መሞከራቸው ነው፡፡ አንድ ነገር ግልፅ ነው፡፡ በአነስተኛ የዝውውር ሂሳብ ቢሆን ኖሮ ሊቨርፑልም ተጨዋቾን አይቀለውም ነበር፡፡ ባርሴሎና በየትኛውም መንገድ ቢሞክር ተጨዋቹ ወደ ኑ ካምፕ ለማምጣት ከፍ ያለ ዋጋ መክፈሉ አይቀሬ ነበር፡፡ በእርግጥ የዝውውር ዋጋው እንዲህ ለፖርቹጋላዊው ሮናልዶ የቀረበ መሆን ነበረበት ወይ የሚለው ያከራክር ይሆናል፡፡ ያለፉት ዓመታት ሪከርዶቹ አስደናቂዎች መሆናቸው ግን ጥያቄ አያስነሳም፡፡
የባርሳ ደጋፊዎች በዝውውሩ ላይ የሚያነሱት ሌላ ጥቄ ዕድሜው ጋር ያያያዛል፡፡ ሮናልዶም ሆነ ቤል በከፍተኛ ሂሳብ ወደ ሪያል ማድሪድ ሲያመሩ ዕድሜያቸው በ20ዎቹ መጀመሪያ ላይ ነበር፡፡ ይህም ማለት ተጨዋቾቹን ሪያል መልሶ መሸጥ ቢፈልግ ተጠቅሞባቸው ለገበያ የሚያቀርብበት ጊዜው ነበረው፡፡ ሱአሬዝ ከዚህ በኋላ ለተጨማሪ የእግርኳስ ህይወት ከባርሴሎና የሚዘዋወርበት ዕድሉ ጠባብ ነው፡፡ ቢዘዋወርም እንኳን ባርሴሎና ለዝውውሩ የከፈለውን ሂሳብ የሚጠጋ ክፍያ አያገኝለትም፡፡ የሱአሬዝ የአሁኑ ዋጋ እጅግ ከፍተኛ መሆኑ እንጂ ክለቦች ፈጣን ስኬት የሚያመጡላቸውን ድንቅ ተጨዋቾች በተመሳሳይ ዕድሜ እያሉ ሊያስፈርሟቸው ይችላሉ፡፡

የሱአሬዝ ጉዳይ ለአሰልጣኝ ለዊስ ኤንሪኬም ራስ ምታት መሆኑ አይቀሬ ይመስላል፡፡ ባርሴሎና ጎል የሚያስቆጥርለት 9 ቁትር አጥቂ መፈለጉ ግልፅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ እንደ ስፔን ብሔራዊ ቡድን ሁሉ የባርሳ አጨዋወትም ለአጥቂ የሚመች አይደለም፡፡ በእርግጥ ይበልጥ የሚቸገሩት አጥቂዎች ብዙ የማይንቀሳቀሱት እና ጎል የማስቆጠር ብቻን ኃላፊነት የሚወስዱት ናቸው፡፡ ሱአሬዝ እረፍት የማያውቅ እና ለቡድን ባላጋራን መጭመቅን መሰረት ያደረገ አጨዋወት የተመቸ ነው፡፡ ጎሎች ማስቆጠር ብቻ ሳይሆን የጎል ዕድሎችን መፍጠርንም ያውቅበታል፡፡ ይህም ማለት ባርሴሎና በፊት መስመር በተመሳሳይ መልኩ ጎል ማስቆጠር እና የጎል እድል መፍጠር የሚችሉትን ሶስት ተጨዋቾች ኔይማር፣ ሱአሬዝ እና ሜሲ በጋራ ይጠቀማል፡፡ በዚህ አሰላለፍ መሰረት አንድሬስ ኢኒዬሽታ ከተለመደው ቦታው ወደ ኋላ አፈግፍጎ እንዲጫወት የሚገደድ ሲሆን ከፊት ያሉት ሶስት ተጨዋቾች ግን ምናልባትም በመላው አውሮፓ አስፈሪውን የአጥቂ መስመር ይፈጥራሉ፡፡

ጥቂት ጊዜ ይወስድ እንደሆነ እንጂ ሱአሬዝ ቡድኑን ጥሩ አድርጎ እንደሚዋሃድ የሚጠራጠር አይገኝም፡፡ ይልቁን የተጨዋቹን ውዝግብ የመፍጠር ባህርይን ክለቡ እንዴት ይለምደዋል የሚለው ጥያቄ ግን ይነሳል፡፡ ባርሴሎና ረብሻ የማያጣውን ተጨዋች እንዴት ሊተማመንበት ይችላል? በዘረኝነት ትንኮሳ ስሙ የተበላሸው እና የሜዳ ላይ ተጋጣሚዎቹን በመንከስ የተኮነነው ተጨዋች ለባርሴሎና ጥሩ ገፅታ ይሆናል?

የዓለም ዋንጫ ድርጊቱን ተከትሎ የተላለፈበት የፊፋ ቅጣትም ሌላኛው ነጥብ ነው፡፡ ሱአሬዝ በቅጣት ምክንያት ከዘጠኝ እስከ 10 የላ ሊጋ ጨዋታዎችን ብቻ ሳይሆን የቻምፒዮንስ ሊግ ግጥሚያዎችም ያመልጡታል፡፡ በእርግጥ ሱአሬዝ ወኪሎች እና ጠበቃዎች የእገዳው መጠን እንዲቀንስ ለማድረግ ተጨማሪ ጫና ለመፍጠር እየተዘጋጁ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ውሳኔውን እንደማይለውጥ ያስታወቀው የእግርኳስ አስተዳዳሪ አካል በቀጣዮቹ ሳምንታት ሃሳቡን መልሶ ያጤነዋል ተብሎ አይጠበቅም፡፡

ከቡድኑ ጋር አብሮ ልምምድ አለመስራቱ በአዲሱ ክለብ በእንግድነት እንዲቀጥል ያስገድደዋል፡፡ ማንኛውም ተጨዋች ወደ አዲስ ክለብ ሲሄድ ከአጨዋወት ፍልስፍናው፣ ከቡድን ጓደኞቹ እና አጠቃላይ ድባቡ ጋር መላመድ ይጠይቃል፡፡ ሱአሬዝ ይህን ዕድል አያገኝም፡፡ በእርግጥ የእገዳውን ዝርዝር የተመለከተ ሰው በዚህ አይደነቅም፡፡ ሱአሬዝ አብሮ አለመለማመድ ብቻ ሳይሆን በኑካምፕ እና ሌሎች ስታዲየሞች ተገኝቶም ጨዋታዎችን ማየት አይችልም፡፡ ስለዚህ እርሱም እንደሌሎች ሰዎች የባርሴሎናን ተጨዋቾች እና ግጥሚያውን በቴሌቪዥን ይመለከታል፡፡ ሌላው ቀርቶ ሱአሬዝ እንደ ቡድን አባልነቱ የባርሴሎና ስኳድ ጋር በውድድር ዘመኑ የመክፈቻ ፎቶግራፍ ከኔይማር እና ሜሲ ጎን ሆኖ አይታይም፡፡ ሌላው ቀርቶ ክለቡ ከዚህ ቀደም ዝለታን ኢብራሂሞቪች፣ ሴስክ ፋብሪጋዝ፣ ኔይማር እና የመሳሰሉትን ከዋክብት ሲያስፈርም በኑ ካምፕ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎችን የሚያስተዋወቅበትን ዕድል በሱአሬዝ አላገኘም፡፡ በአጠቃላይ አጥቂው አሁን ከሊቨርፑል እዳነት ወደ ባርሴሎና ችግርነት ተለውጧል፡፡

‹‹በ16 ዓመት የሊቨርፑል ቆይታዬ ሱአሬዝ፣ ማይክል ኦዌን እና ፈረንናዶ ቶሬስ አብረውኝ ከተጫወቱት አጥቂዎች ሁሉ ምርጦቹ ናቸውው፡ እኔ የዋናው ቡድን አባል ስሆን ሮቢ ፎውለር በብቃቱ ጫፍ ላይ አይገኝም ነበር፡፡ ከሁሉም ግን ሱአሬዝ የተሻለው አጥቂ ነው›› የሚለው የቀድሞው የክለቡ ተከላካይ ጃሚ ካራገር ነው፡፡

‹‹ሉዊስ በሜዳ ላይ የሚሰራቸውን ነገሮች አይተህ በአድናቆት ከመዋጥ ሌላ ምንም መናገር አትችልም፡፡ አሁን ግን ጥያቄው ይህ ነው፡፡ በአንፊልድ ያገኘው የነበረውን አድናቆት እና ክብር በኑካምፕ ያገኛል? ወይስ እንደ ኦዌን እና ቶሬስ ፍቅርን እና የመርሲሳይድ የጎል ሪከርዱን አጥቶ ይንከራተታል? ኦዌን እና ቶሬስ በአንፊልድ የሰሩትን ገደል በሌላ ቦታ ለመድገም የመቸገራቸው አንዱ ሰበብ ይህ ነበር፡፡

‹‹እንደ እኔ ግምት ወደ ሪያል ማድሪድ ቢሄድ ኖሮ ነገሮች ይበልጥ ይመቹት ነበር፡፡ በእርግጥ ሮናልዶ ትልቅ ተጨዋች ነው፡፡ ነገር ግን ሉዊስ ከካሪም ቤንዜማ የተሻለ አጥቂ በመሆን ቦታውን የራሱን ማድረግ ይችል ነበር››
ካራገር የተጫዋቹን ወደ ካታሎኒያ መሄድ ያልወደደበት ምክንያት የባርሴሎና ወግ አጥባቂ ደጋፊዎች ከሚያቀርቡት ጋር ባይመሳሰልም የአጥቂው ዝውውር ሁሉንም ወገኖች ቅር ማሰኘቱ ግን ግልፅ ነው፡፡ የባርሳ ባለስልጣናት ሱአሬዝን ማስፈረማቸው ብቻ ሳይሆን ለግዢ አስቀድመው ማሰባቸው በራሱ ያስገረማቸው የሚመስሉ የክለቡ አፍቃሪዎችም አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ባርሳ በሱአሬዝ ፊርማ ሜዳ ላይ ራሱን አጠናክሮ ከሜዳ ውጪ ለውርደት መዳረጉን ያብራራሉ፡፡

የባርሴሎና ቦርድ ወቅታዊ ትልቅ እቅድ ግልፅ ነው፡፡ ቡድኑ ወደ አሸናፊነቱ መመለስ አለበት፡፡ ይህንን ለማሳካት በምርጥ ተጨዋቾች የተሰራ ምርጥ ቡድን ያስፈልጋል፡፡ የክለቡ ባለስልጣናት እቅዳቸውን ከግብ ለማድረስ ሲሉ ባርሴሎና የኖረለት ባህሉን እና መልኩን እየጠፋ መሆናቸው ይወራባቸዋል፡፡ የአሌክሲስ ሳንቼዝን 9 ቁጥር ማሊያ ለሱአሬዝ ሰጥተው የቡድኑን ጥንካሬ ሲያሻሽሉ የክለቡ ታሪክ እና ዓለም አቀፍ ገጽታ አበላሽተዋል፡፡ ሳንድሮ ሮሴል በኔይማር ውስብስብ የዝውውር ሂደት መሳቂያ ያደረጉት የባርሴሎና ስም አሁን በሱአሬዝ የግል ተጠባቂ ችግሮች ይበልጥ እንዳያድፍ ያሰጋል፡፡
ሱአሬዝን ባለፉት ዓመታት የሚያውቀው ሁሉ ተጨዋቾ ምን ያህል በተደጋጋሚ ችግሮችን የመፍጠር አቅም ያለው ሰው እንደሆነ ይገነዘባል፡፡ ሜዳ ላይ የጨዋታን ዳኛ ገፍትሮ በቴስታ ሲማታ ገና የ16 ዓመት ልጅ ነበር፡፡ በእግርኳስ ህይወቱ በአውሮፓ ሊጎች በፕሮፌሽናልነት መጫወት ከጀመረ ወዲህ ብቻ ሶስት ሰዎችን ነክሷል፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ በዘረኝነት ሜዳ ላይ ባላጋራውን መተንኮሱ ሳያንስ እስካሁንም ይቅርታ ለመጠየቅ ፈቃደኛ ሆኖ አልተገኘም፡፡ አሁን የተጣለበትን ቅጣት ጨምሮ ከ2010 ወዲህ በእገዳ ምክንያት የሚያልፉት ጨዋታዎች ብዛት 48 ደርሷል፡፡ እነዚህን ጨዋታዎች የተቀጣው የቀይ ካርድ ሳይመዘገብበት መሆኑን ልብ በሉ፡፡ እስከመጪው ኦክቶበር የባርሴሎናን ማሊያ ለብሶ ሜዳ ላይ አይታይም፡፡

ይህ ሁሉ የሚያስጨንቅ ጉዳይ አይመስልም፡፡ ሮሴል፣ ፔፕ ማሪያ ባርቶሜኡ፣ አንዶኒ ዙቢዛሬታ እና ሌሎችም የቦርዱ ሰዎች የቡድኑ ውጤት ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ደጋግመው ይናገራሉ፡፡ ባርሴሎና በሜዳ ላይ ተፎካካሪነቱን ይዞ እንዲቀጥል ቡድኑን ማጠናከሪያ ገንዘብ ለማግኘት በሚሉ ተመሳሳይ ሰበብ የካታር ኢንቨስትመንት የንግድ ምልክትን ከክለቡ መልክ ጋር የቀላቀሉት እነዚሁ ሰዎች ናቸው፡፡ በዓለም ሊግ ምርጥ ተስፈኛ የሚባለው ተጨዋች ለሪያል ማድሪድ እንዳይፈረም በሚል ብቻ በርካታ ህጎችን ለመጣስ የሚደፍሩትም እነርሱ ናቸው፡፡ አሁን ደግሞ 95 ሚሊዮንዩሮ የሚጠጋ ገንዘብ አውጥተው የወቅቱን የዓለማችን የተጠላ፣ ይቅርታ ያልተደረገለት እና ብዙዎች ጀርባቸውን የሰጡትን ተጨዋች አምጥተዋል፡፡

የክለቡ ቦርድ እና ሱአሬዝ ከተቀሩት የክለቡ ተጨዋቾች ጋር ተባብረው ዋንጫዎችን ማሸነፋቸውን ይቀጥላሉ፡፡ ባርሴሎናም እንደ ፔፕ ጋርዲዮላ ዘመን የሰዎችን ልብ ገዝቶም ባይሆን ማሸነፍ ይቀጥላል፡፡ በተመሳሳይ የማይቀጥል አንድ ነገር ግን አለ፡፡ ‹‹ባርሴሎና ከክለብም በላይ!›› የሚለው ስም፡፡

↧

ኢትዮጵያውያን በሙኒክ አንድ ላይ “ላንቺ ነው ኢትዮጵያን”ዘመሩ

$
0
0

ሰሞኑን በጀርመን ሙኒክ በተደረገ በአውሮፓ የኢትዮጵያ ስፖርትና ባህል ፌስቲቫል መዝጊያ ላይ ስሜታዊ የሆነ እንቅስቃሴ ታይቷል። ይኸውም “ላንቺ ነው ሃገሬ” የሚለውን ዘፈን ሕዝቡ አብሮ በመዝፈን አንዳንዶቹ ተቃቅፈው ሲላቀሱ የሚከተለው ቪድዮ ያሳየናል። እንመልከተው።

ኢትዮጵያውያን በሙኒክ አንድ ላይ “ላንቺ ነው ኢትዮጵያን” ዘመሩ

↧

Health: ስለኢቦላ በሽታ ማወቅ ያለብዎ 10 ነገሮች

$
0
0

ebola

1. የኢቦላ በሽታ ምንድ ነው?
የኢቦላ በሽታ በቫይረስ ምክንያት የሚመጣ፣ በፍጥነት ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፍና በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሞት የሚዳርግ በሽታ ነው፡፡ የኢቦላ በሽታ በምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በተደጋጋሚ በመከሰት ከፍተኛ ህመምና ሞት እያደረሰ የሚገኝ በሽታ ነዉ፡፡ በሽታው በማንኛውም ወቅት በአገራችንም በወረርሽኝ መልክ ሊከሰት የሚችል በመሆኑ ከወዲሁ ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ ይሆናል፡፡ የኢቦላ በሽታ ለከፍተኛ ህመምና ለሞት የሚዳርግ ቢሆንም መከላከል ግን ይቻላል፡፡

2. የኢቦላ በሽታ መተላለፊያ መንገዶች፡-
•በኢቦላ ከታመመ ሰው ቁስል፣ ደም፣ ምራቅ፣ ትውከት፣ አይነምድርና ሽንት ጋር በቀጥታ በመነካካት ወይም እነዚህ ፈሳሾች ወደ ጤነኛ ሰው አይን ከተረጩና ከገቡ፣
•ንጽህናቸው ባልተረጋገጠ ወይም ሌሎች ህሙማን የተጠቀሙበትን መርፌ ሳይቀቅሉ በመጠቀም፣
•የኢቦላ በሽታ ታማሚ የተጠቀመባቸዉን ስለታማ መሳሪያዎች በመጠቀም፣
•በኢቦላ በሽታ የሞተ ሰውን አስከሬን በቀጥታ በመነካካት፣
•በኢቦላ በሽታ የሞተውን እንሰሳ ስጋ በመመገብ ናቸው፡፡

3. በኢቦላ በሽታ የተያዘ ሰው የበሽታዉን ምልክቶች የሚያሳያው መቼ ነው?
በኢቦላ በሽታ ከተጠቃ ሰው ጋር ንኪኪ የፈጠረ ሰው ከ 2 እስከ 21 ቀናት ባለዉ ጊዜ ውስጥ የበሽታውን ምልክቶች ማሳየት ይጀምራል፡፡

4. በኢቦላ በሽታ የተያዘው ሰው የሚያሳያቸው ምልክቶችና ስሜቶች፡-
•ድንገተኛና ከፍተኛ የሆነ ትኩሳት ይይዘዋል፡፡ በተጨማሪም ማስመለስ/ትውከት/፣ ተቅማጥ፣ ራስ ምታት፣ የቆዳ ሽፍታ እና የአይን ቅላት ምልክቶች ይታዩበታል፡፡
•በሰውነታችን ክፍት ቦታዎች ማለትም አይን፣ አፍንጫ፣ ድድ፣ ጆሮ፣ ፊንጢጣና በብልት በኩል የመድማት ምልክት ሊታይም ላይታይም ይችላል፡፡

5. በኢቦላ በሽታ መያዙ የተጠረጠረ ወይም የተያዘ ሰው ከገጠመን ምን ማድረግ አለብን?
•ታማሚውን በምንረዳበት ጊዜ ሰውነታችንን ከበሽታው መከላከል የሚያስችለንን የእጅ ጓንት፣ የአይን መከላከያ መሳሪያ (ጎግል) እና የአፍንጫና የአፍ መሸፈኛ ማስክ መጠቀም፤
•የታመመውን ሰው ወድያውኑ ለአስፈላጊ ህክምናና እርዳታ በአቅራቢያው ወደሚገኘው ጤና ተቋም መወሰድ፤
•በኢቦላ በሽታ የተጠረጠረ ሰው በሚገኝበት ወቅት ወድያውኑ በአቅራቢያው ወደሚገኘው ጤና ተቋም ወይም ጤና ጽ/ቤት ሪፖርት ማድረግ፣
•በበሽታው መያዙ የተጠረጠረ ወይም የታመመ ሰው የተጠቀመባቸዉን አልባሳትና መኝታውን በበረኪና ማጠብ ይኖርብናል፡፡

6. ለኢቦላ በሽታ ተጋላጭ የሆኑት ማናቸው?
•በሽታዉ ከታመመ ሰው የሚወጣውን ደምና ሌሎች የሰውነት ፈሳሾች በቀጥታ በመነካካት የሚተላለፍ በመሆኑ ከታመመው ሰው ጋር የሚኖር ማንኛውም ሰው በበሽታዉ ሊያዝ ይችላል፡፡
•በሽተኛውን በሚመግቡበትና በሚንከባከቡበት ወቅት የእጅ ጓንትና ሌሎች መከላከያ መሰሪያዎች ሳያደርጉ ከሰውነት ፈሳሽ ጋር ንክኪ የሚፈፅሙ ሰዎች በቀላሉ በበሽታው ሊያዙ ይችላሉ፡፡
•በኢቦላ በሽታ የሞተውን ሰው አስከሬን ያለ እጅ ጓንትና ሌሎች የመከላከያ መሳሪያዎች የምንነካካ ከሆነ በቀላሉ በበሽታ ልንጠቃ እንችላለን፡፡

7. የኢቦላ በሽታን እንዴት ልንከላከል እንችላለን?
•የእጅ ጓንት፣ የአይን ጎግል እና ሌሎች የሰውነት መከላከያ መሳሪያዎችን በመጠቀም በበሽታው ከተጠቃ ሰው ውስጥ ከሚወጣው ማንኛውም ፈሳሽ ጋር በቀጥታ ባለመነካካት፤
•ያለ እጅ ጓንት በበሽታው የተጠቃውን ሰው ቁስል አለመንካት፤
•በኢቦላ በሽታ የተያዘው ሰው የተጠቀመውን መርፌና ሌሎች ስለት ያለቸውን መሳሪያዎች አለመጠቀም፤
•በኢቦላ በሽታ መያዙ የተጠረጠረና የሞተ እንስሳን ሥጋ አለመመገብ፤
•በኢቦላ በሽታ የሞተን ሰው አስከሬን ያለጓንትና ሌሎች የመከላከያ መሰሪያዎች ያለመንካት፣ የቀብር ሥነ ሥርኣቱም በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈፀም ማድረግ ፤ እንዲሁም ከቀብር በኋላ ያለውን ስነስርዓት ማሳጠር፤
•የታመመውን ሰው ከረዳን ወይም በበሽታዉ ምክንያት የሞተውን ሰው አስከሬን ከነካን በኋላ እጃችንን በውሃና በሳሙና በደንብ መታጠብ፣

8. በቤት ውስጥ መወሰድ ያለበት ጥንቃቄ ፡-
•በኢቦላ በሽታ የተጠቃ ወይም የተጠረጠረ ሰውን በተቻለ መጠን ለብቻው በተዘጋጀ ቦታ መለየት፣
•በበሽታው የተጠቃ ወይም የተጠረጠረን ሰው ወደ ጤና ተቋማት በምንወሰወድበት ወቅት ከታማሚው ጋር አላስፈላጊ ንክኪ አለማድረግ፣
•በበሽታው ከተጠቃ ወይም ከተጠረጠረ ሰው ወይም የሰውነት ፈሳሽ ጋር ንክኪ ከተፈጠረ ወዲያውኑ እጃችንን በውሃና በሳሙና መታጠብ፣
•በኢቦላ በሽታ የተጠቃውን ሰው በምንረዳበት ወይም በምንንከባከብበት ወቅት የእጅ ጓንት፣ የአይን ጎግል፣ የፊት መሸፈኛ እና ሌሎች የሰውነት መከላከያ መሳሪያዎችን መጠቀም፣
•በበሽታው የተጠቃ ወይም የተጠረጠረ ሰው የሰውነት ፈሳሽ መሬት ከበከለ በረኪና ይጨምሩበት፤ ከ15 ደቂቃ በኋላም ይፀዳ፤ በቆሻሻ የተነካኩ ቁሳቁሶችና አልባሳት መቃጠል ይኖርባቸዋል፣
•በኢቦላ በሽታ ታሞ የሞተ ሰው የቀብር ስነስርዓት ሲፈፀም ከአስከሬን ጋር ንክኪ አለማድረግ፣ የጋራ እጅ መታጠቢያም አለመጠቀም፣
•የቀብር ስነስርዓት ሲፈፀም አስከሬኑ በፕላስቲክ ከረጢት መጠቅለል፣ የቀብር ስነስርዓት ሲፈፀም በሰለጠነ የጤና ባለሙያ ምክር መታገዝ፣

9. በሽታው ወደ ሀገራችን ሊገባ የሚችልባቸዉ ሁኔታዎች፡-
በሽታው እስከ አሁን በሀገራችን ያልታየ ቢሆንም በምዕራብ አፍሪካ ሀገሮችና በሀገራችን መካከል ባለው የህዝብ እንቅስቃሴ ምክንያት በማንኛውም ጊዜ ወደ አገራችን ሊገባ ይችላል፡፡ በተለይም በኤርፖርቶችና በድንበር አከባቢ ባሉ መውጫና መግቢያ በሮች በኩል ሊገባ የሚችልበት አጋጣሚ ሊፈጠር ስለሚችል አስፈላገው ጥንቃቄ መደረግ ይኖርበታል፡፡

10. እየተወሰዱ ያሉ እምጃዎች
በሽታው እስከ አሁን ወደ ሀገራችን ባይገባም ከወዲሁ ለመከላከልና ከተከሰተም አፋጠኝ ምላሽ መስጠት እንዲቻል በቂ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር በአየር መንገዱ የሚጓዙ መንገደኞችን ጤንነት ሁኔታ መለየት፣ የታመመ ሰው ከተገኘም ወዲያውኑ ህክምና የሚያገኝበት ሁኔታ ተመቻችቷል፡፡ እንዲሁም የህክምና ግብዓቶችና ለባለሙያዎች የሚሆን የመከላከያ መሳሪያዎች ተለይተው በመሟላት ላይ ይገኛሉ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ ጤና ተቋማት ለተውጣጡ የጤና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ውስጥ መስጠት ዝግጅት ተጠናቋል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ፡-
ዶ/ር ዳዲ ጅማ -በስልክ፡ +251911247092
አቶ አህመድ ኢማኖ – በስልክ፡ +251912673924 ማነጋገር ይቻላል
ከኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ።

↧
↧

አሜሪካ ለአፍሪካ 33 ቢሊዮን ዶላር አሰባሰበች

$
0
0

እኛ ከአፍሪካ የተፈጥሮና የከርሰ-ምድር ሃብቷን ብቻ ፈልገን ሳይሆን በቅድሚያ የምናየውና የምንተማመንበትም የሰው ሃብቷ ነው ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በአፍሪካ ላይ ያላቸውን የወደፊት ተስፋና እምቅ አቅም አድንቀው ተናግረዋል፡፡

የእርሣቸው መንግሥት ፍላጎት በአፍሪካና በአሜሪካ መካከል ያለው2ን ሥራና መተጋገዝ አሁን ባለው ሁኔታ እንዲቀጥል ማድረግ ሳይሆን ከፍ ወዳለ ደረጃ እንዲሸጋገር መሥራት ነው ብለዋል፡፡

በመላ አፍሪካ ለሚንቀሣቀሱ የግልና የመንግሥት አጋርነት ሥራዎችን ለማገዝ የተገኘው ገንዘብ ዋሺንግተን ዲሲ ላይ እየተካሄደ ላለው የአሜሪካ-አፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ ትናንት እርሣቸው ንግግር ያደርጉ እስከነበረበት ጊዜ 33 ቢሊየን ዶላር መድረሱን አስታውቀዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

C105BA12-CF28-4FBA-A888-2F75E128219E_w640_r1_s

↧

በአራዳ ምድብ ችሎት ሐብታሙ አያሌው ዳንኤል ሺበሺና የሺዋስ አሰፋ

$
0
0

የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት
አራዳ ፍርድ ቤት ዛሬ እንዲህ ሆነ

1907817_322894797874878_2914052661791867899_oዛሬ ከቀኑ 8፡00 በአራዳ ምድብ ችሎት ሐብታሙ አያሌው ዳንኤል ሺበሺና የሺዋስ አሰፋ እንደሚቀርቡ በመነገሩ ብዛት ያላቸው ሰዎች ቀደም ብለው በፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ ተገኝተው ነበር፡፡ፖሊስ በፍርድ ቤቱ የተሰጠውን የቀጠሮ ሰዓት አክብሮ እስረኞቹን ማቅረብ በመቻሉ ላይ ብዙዎች ስጋት የነበራቸው ቢሆንም አልተሳሳቱም፡፡

መደበኛው የስራ ሰዓት ከተጠናቀቀ በኋላ ከፍተኛ ታጣቂ ሃይል የፍርድ ቤቱን ቅጥረ ግቢ ተቆጣጠረው ከደቂቃዎች በኋላም አንድ ማንነቱን ቀደም ብለን ለማወቅ ያልቻልነው ቀጠን ያለ ወጣት እጆቹን ታስሮ ወደ ችሎት ገባ፡፡በኋላ ላይ ማረጋገጥ እንደቻልኩት ወጣቱ ዘላለም የሚባል ሲሆን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የማስተርስ መርሀ ግብር ተማሪ ነበር፡፡ፖሊስ በተመሳሳይ መልኩ እነ ሐብታሙን በያዘበት ዕለት በቁጥጥር ስር መዋሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በመለጠቅም ዳንኤል ሺበሺ ሁለት እጆቹ በካቴና ታስረው ነጠላ ጫማ ፣ጥቁር ሱሪና ቱታ ጃኬት ተላብሶ ወደ ውስጥ ዘለቀ፡፡

ከጺሙ ማደግ በስተቀር ዳንኤል ፊትና አካል ላይ ምንም አይነት ለውጥ አይታይም፡፡ስሙን እየጠሩና በእጆቻቸው እያጨበጨቡ አድናቆታቸውን ለሚገልጹለት ሰዎች ጥርሱን ብልጭ እያደረገ አጸፌታውን ከመመለስ ውጪ ምንም አልተናገረም፡፡

የዳንኤልን ችሎት ለመከታተል ጋዜጠኞችና ቤተሰቦቹ ጥያቄ አቅርበው አይቻልም የሚል ተሰጥቷቸው የነበረ ቢሆንም ጉዳዩን የተመለከቱት ሴት ዳኛ ቤተሰቡ እንዲገባ በማዘዛቸው ባለቤቱ ችሎቱን ተከታትላለች፡፡

የዳንኤል ጉዳይ እየታየ በነበረበት ሰዓት የሺዋስ አሰፋን የያዘችው መኪና ፍርድ ቤት ቅጥር ግቢ ደረሰች፡፡ለደቂቃዎች ያህልም የሺዋስ በመኪናው ውስጥ እንዲቆይ ተደረገ፡፡ዳንኤልና ዘላለም እንደጨረሱና ግቢውን እንዲለቁ ከተደረጉ በኋላ የሺዋስ እንዲገባ ተደረገ፡፡ሙሉ ነጣ ያለ ቱታ ያጠለቀው የሺዋስ ግቢው ውስጥ እንደገባ ደመቅ ያለ ጭብጨባና በርታ የሚሉ መልእክቶች ጎረፉለት፡፡ፖሊሶች በጭብጨባውና በመልእክቶቹ ደስተኞች አለመሆናቸውን ቢገልጹም ከውስጥ ፈንቅለው የሚወጡ ስሜቶችን በቁጣና ማስፈራሪያ ሊያስቆሙ እንደማይችሉ የተረዱ ይመስሉ ነበር፡፡

የሺዋስ እንደሁልገዜው ዘና ያለና የተረጋጋ ነው፡፡ፈገግታውን በመርጨትና ሰላምታ በመለገስ የታሰሩ እጆቹን እያወዛዘወዘ ችሎት ገባ፡፡የሺዋስ የውስጥ ጉዳዩን ከውኖ እንደጨረሰም በተመሳሳይ የወዳጆቹና የትግል አጋሮቹ ጭብጨባና አድናቆት ታጅቦ ግቢውን ለቀቀ፡፡
በመጨረሻም ሐብታሙ አያሌው ወደ ውስጥ እንዲገባ ተደረገ፣ ሐብታሙ እግሮቹ ግቢውን እንደረገጡ ተሰብስበው ለጠበቁት ሰዎች ጥልቅ ፈገግታውን በመለገስ ሰላምታ አቅርቧል፡፡‹‹እንወድሃለን፣አይዞን››የሚሉ ቃላት ከደማቅ ጭብጨባ ጋር በግቢው አስተጋቡ፣ አጃቢዎቹም ፈጠን እንዲል እየወተወቱት ችሎት አስገቡት፡፡

ከወጣት ዘላለም በስተቀር በዕለቱ ችሎት ጠበቃ ተማምና ገበየሁ ታሳሪዎቹን ወክለው ቀርበዋል፡፡ሀብታሙ በመጣበት አጀብ ግቢውን እንዲለቅ ከተደረገ በኋላ ሁለቱ ጠበቆች ‹‹ተለዋጭ ቀጠሮ ለነሀሴ 26/2006 መሰጠቱን አውስተዋል፡፡ፖሊስ በዛሬው ችሎት በተጠርጣሪዎቹ ላይ ምንም አይነት ማስረጃ አለማቅረቡን መረጃ ለማሰባሰብ እንዲረዳው የጠየቀው ቀን እንደተሰጠውም አብራርተዋል፡

↧

የአቶ በረከት የዛሬ ውሎ፤ ባለስልጣኑ ለደህነታቸው ጥበቃ ከሆስፒታል መልስ የጅዳን ቆንስላ ጽ/ቤት ዛሬ ጎበኙ

$
0
0

Bereket Simon weeping with his wife over Meles Zenawi's death
Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ
አቶ በረከት ስሞኦን ከሆስፒታል ቀጠሮአቸው መልስ ዛሬ የጃዳ ቆንስላ ጽ/ቤትን ለመጀመሪያ ግዜ መጎብኘታቸው ታውቋል ። አቶ በረከት እግር መንገዳቸውን ለዲፕሎማቱ ስለጤንነታቸው ሁኔታ ገለጻ እንዳደረጉ ከቆንስላው ጽ/ቤት የወጡ ምስጢራው መረጃዎቻችን ያመለክታሉ:: አቶ በረከት ስሞን በሼክ መሃመድ አላሙዲን የግል አውሮፕላን በሚስጠር ሳውዲ አረቢያ ለህክምና ከገቡ ወዲህ ለደህነታቸው ሲባል ሃገርቤት ካሉ የመንግስት ከፍተኛ ባለ ስልጣናተም ሆነ እዚህ ሳውዲ አረቢያ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት እምነት ጥሎባቸው ሃገር እና ህዝብን ወክለው ከተቀመጡ ዲፕሎማቶች በስልከም ሆነ በአካል ሳይገናኙ በድብቅ የልብ ህክምና ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወሳል ።

እኚሕ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ሳኡዲ አረብያ ጅዳ ለህክምና መግባታቸውን ተቃዋሚ ከሚሏቸው ከሶሻል ሚዲያዎች ያረጋገጡት የቆንስላው ዲፕሎማቶች አቶ በረከት ስሞኦን በፈጸሙት ስህተት ሲበሳጩ መስተዋላቸውን ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል። የአቶ በረከት ስሞን ለህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ ጅዳ መግባትን ተከትሎ በሶሻል ሚድያ በመናፈሱ ባለስልጣኑ ህክማናቸውን በአግባቡ መከታተል እንዳልቻሉ በወቅቱ መዘገቡ ይታወሳል።

ከዛሬው የሆስፒታል ቀጠሮ መልስ በኋላ ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ጎራ ያሉት አቶ በረከት ለቆንስላው እና ለዲፕሎማቱ እውቅና ክበር ከመስጠት ሳይሆን ባለስልጣኑ ከሆስፒታል ከወጡ ወዲህ የተለያዩ ሆቴሎችን በመከራየት በድብቅ ሲያስታምሞቸው እና ድጋፍ ሲያደርጉላቸው የከረሙት ሼክ አላሙዲን ከሁለት ቀን በፊት ለስራ ጉዳይ ወደ አሜሪካ መብረራቸውን ተከትሎ የጤንነታቸው ሁኔታ እንብዛም አስተማማኝ ያልሆነው እኚሕ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ወደ ሃገር እስኪመለሱ ለደህነታቸው ጥበቃ እንዲያደርግላቸው የዘየዱት መላምት መሆኑ ከቆንስላው ጽ/ቤት የወጡ መረጃዎች ያስረዳሉ።

ባለስልጣኑ አርፈውበታል የተባለው ሆቴል ማማሻውን በማቅናት መረጃ ለማሰባሰብ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም ።

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live




Latest Images