ከማዕከላዊ ኮሚቴ ውጭ ያሉ የኦህዲድ ካድሬዎች አሁኑኑ ወስዳችሁ እሰሩን እያሉ ነው ።
==========================================
አዲሱ የኦህዲድ ሊቀመንበር ከማዕከላዊ ኮሚቴ ውጭ ያሉትን የኦህዲድ መካከለኛ እና ከፍተኛ ካድሬዎች ሰሞኑን ሰብስበው ነበር።በስብሰባው ላይ ከተነሱት ሃሳቦች መካከል
1የፌደራሉን መንግሥት ባለሥልጣናት እናንተ ከፈራችሁ እኛ እንህድ እና የህዝባችንን ብሶት እናቅርብ
2 እየተናገርን ያለነው ተቀርፆ ይሰጣቸው ።ከአ.አ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ ተደጋግሞ ስማቸው ለምነሳው የፌደራል ባለስልጣናት ይህንን ማልዕክታችንን ቀርፃችሁ አቅርቡልን።ይህንን መጨማለቃቸውን እንድያቆሙ ንገሩአቸው።ከፈራችሁ ደግሞ ይህንን ቭድዮ ውሰዱ እና አሳዩአቸው።
3 ኃይለማሪም ከስልጣን መልቀቅ አላበት።
4 ህዝብ ልበላን ነው።እናንተ የፌደራል ባለሥልጣናትን ትፈራላችሁ።ሥለዚህ በህዝብ ከምንበላ ውሰዱ እና እሰሩን።ከሞት የተረፍነው በጎሳችን ምክንያት ነው እንጅ በኦህዲድ ምክንያት አይደለም።ስለዚህ እናንተ ከፈራችሁ ከምንሞት እኛው ሄደን እንጋፈጥ።
5 የኦሮሞ ህዝብን ደም ኢህአዲግ በምንም መልኩ ልመልስ አይችልም ።ስለዚህ ይህንን ይተው።ይህንን ይቅርታ መጠየቅ ዋጋ የለውም።ምናልባት ከፈለገ ኢህአዲግ በሙስልሙ ህብረተሰብ ላይ ያደረሰውን በደል ይቅርታ ይጠይቅ።
ብቻ በአጠቃላይ ካድሬው (እሥከ ሚንሥትሬ ዴታ ያለበት ) እሳት ለብሶ እሳት ጎርሶ አሁኑን ወስዳችሁ ካላሰራችሁን እያለ ትላንት አዳማን ተሰናብቶ ወደየሃገሩ አቅንቷል።
#OromoProtests #Ethiopia