(ኤፍ.ቢ.ሲ) ዛሬ ማምሻውን 11 ሰዓት ተኩል አካባቢ የሰሌዳ ቁጥሩ 03 46206 አዲስ አበባ የሆነ ሀይገር አውቶብስ ከፒያሳ ወደ ለገሃር ሲያቀና ቴዎድሮስ አደባባይ ጋር ሲደርስ ተገልብጧል።
ከእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከል እና መቆጣጠር ባለስልጣን የህዘብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ እንደገለፁት፥ በአደጋው 13 ሰዎች ከባድ አደጋ ደርሶባቸው ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።
የባለስልጣኑ አምስት አምቡላንስ ተሽከርካሪዎችም የተጎዱትን ወደ ህክምና ተቋማት አድርሰዋል።
እሰካሁን በአደጋው የአንድ እግረኛ ህይወት ማለፉንም ጠቅሰዋል።
The post ሀይገር አውቶብስ ፒያሳ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ ተገልብጦ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ 13 ሰዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል appeared first on Zehabesha Amharic.