ትላንትና የአንድነት ሃይል ነን ሁላችን ለኢትዮጵያችን ሲሉን የነበረ ስለኦሮሞ ሕዝብ መበደል አቤት ሲባል ኦሮሞ መሆኔን ወደ ኢትዮጵያዊ መሆኔ/ሰው መሆኔ ይቀየር ብለው የሰብዐዊነት ዘመቻዎችን በጥፊ ለማላጋት የተንደረደሩ ኦሮሞ አሊያም ሌላው ብሄር ሲጠራ ጀመሩ ዘረኝነት የሚሉ አተፍታፊዎች ኢትዮጵያ ብለው በስሟ የሚነግዱ ጥቂቶች ዛሬ ላይ አማራው ይደራጅ አሊያም ይገንጠል እያሉ ማራገባቸው የፖለቲካ ስትራቴጂ አይሉት የድል ግብ ምን ያህል ማንነታቸውን ገልጸው እንዳወጡ በይፋ አይተናል::በእምነቶች ዙሪያ የሚደረጉ ትግሎችን ውስጥ ውስጡን ለማክሰም ሲራወጡ ያየናቸው አዛኝ ቂቤ አንጓቾች ድፍርስ የፖለቲካ ባህሪያቸውን አደባባይ ላይ እያስነበቡን መሆኑ ለሽሙጥ ዳርጓቸዋል::
ራሳችንን ወደ አንድነት እንምራ አምባገነኖችን ታግለን ሕዝቦችን እይመራን ነጻ እንውጣ…መስመራችን ለአንዲት ኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያን ጥርጊያ እያበጀን እሾህ እና አሜኬላ እየነቀልን ወያኔን ከነግሳንግሱ በጋራ ተባብረል በአንድነት ሃይላችን እናስወግድ የጎሳ ፖለቲካ ከቅኝ ገዢዎች የተወረሰ የመከፋፈያ እና ሕዝቦችን የመርገጫ መሳሪያ ነው እያልን ባለንበት ሰአት እየተወያየን ለትግላችን በምንተባበርበት እና የዳበረ የሰለጠነ ሃሳብ በምናፈልቅበት ወሳኝ ወቅት ላይ የወያኔን የጎሳ ፖለቲካ ልዩ መርዛዊነት ታከን ለመደራጀት ሲከፋም ለመገንተል ማሰባችን የምንሄድበት መንገድ አለማወቅ ብቻ ሳይሆን ከጭቃ ወደ እሾሃማ ሽቃ እያዘነበልል መሆኑን ልንረዳው ግድ ይላል:: ትላንት የአንድነት ሃይል ነን የሚሉ ግሳንግሶች ዛሬን ስለመገንጠል እና ስለ ጎሳዊ መደራጀት ሊሰብኩን ሲሞክሩ ምሞከራቸው ጤነኝነታቸውን እንድንጥራጠር አድርጎናል::
ወያኔ የሚፈልገው እኮ የታገለለትም አላማ እኮ ይህ ነው:: በጎሳ ምከፋፈል ማደራጀት ማስገንጠል ማገነጣጠል በይፋ በፖለቲካ ፕሮግራሙ እና ግልባጩ በሆነው ህገመንግስቱ ላይ በግልጽ ሰፍሮ ከመታየቱም በላይ ከአመት እስከ አመት የሚሰበከው በውጪም በሃገር ውስጥም ለኢትዮጵያውያን የተሰጠው የቤት ስራ ይሕው በጎሳ እንደራጅ ንገንተል የሚለው መርዘኛ ፕሮፓጋንዳ ሲሆን ህዝብንም እየለያየ የሚያፋጀው የሚያፈናቅለው የሚያሰድደው መኖሪያ አሳጥቶ የሚያንከራትተው የሚያሳስረው የሚያስገድለው ወዘተ ይኸው ከይሲ አስተሳሰብ ነው::ኢትዮጵያውያን በጋራ በአንድነት ተያይዘን የወያኔን አምባገነን ዘረኛ መንግስት እናስወግድ ብለን ከዳር እስከዳር እያስተባበርን እየቀሰቀስን ባለንበት ወቅት ላይ አደፍራሽ ሃሳቦችን በማራገብ የወያኔን የቤት ስራ ለመስራት መራወጥ ወንጀለኝነት እና የትግል አደፍራሽነት ቢሆንም የዚህ ሃሳብ ባለቤቶች ሩጫ ወንዝ እንዳማያሻግራቸው እና እንደማይሳካላቸው አስረግጠን ልንነግራቸው ይገባል::የወያኔ መደምሰስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የወያኔ ሃሳቦችን ሆኖ ቦምቦች አብረው የሚከሽፉበት ጊዜ ሩቅ አይደለም:: ድል የሕዝብ ነው::መነጣተል አሊያም መገነጣጠል ብሎም በጎሳ ፖለቲካ መደራጀት የምትሉ እናንተ በፖለቲካ እና በኢኮኖሚ እየተበደለ በገዢዎች አለንጋ ለሚገረፈው ደሃው ወገናችን እዘኑለት::
The post ዛሬም ታጥቦ ጭቃ … !!!! ወያኔም የሚፈልገው ይህንን እኮ ነው:: appeared first on Zehabesha Amharic.